Quantcast
Channel: Ethiopian News | ዘ-ሐበሻ | Latest News Provider | News For All
Viewing all articles
Browse latest Browse all 15006

የጽዮንን በዓል አክብረው ከተመለሱ ምዕመናን ውስጥ መኪና ተገልብጦ የአራት ሰዎች ሕይወት አለፈ

$
0
0

ከዘመድኩን በቀለ

በየዓመቱ ህዳር 21 ቀን በታላቅ መንፈሳዊ ሥነሥርዓት የሚከበረውን የህዳር ጽዮን በዓል ለማክበር ከአዲስ አበባ ተነስቶ የነበረው የአቡነ አሮን መንፈሳዊ የጉዞ ማኅበር መኪና 60 ተጓዥ ምእመናንን ይዞ ከበዓሉ መልስ ዛሬ ከወልድባ ሰቋር ጉብኝት በኋላ ወደ ጎንደር በመመለስ ላይ ሳለ ከአንባ ጊዮርጊስ ወጣ ብሎ ልዩስሙ 44 ተብሎ ከሚጠራው ሥፍራ ላይ አደጋ ደርሶበት ብዙ ሰው ተጎዳ ።
axum
በአደጋው እስካሁን 3 ተጓዥ መንገደኞች ሕይወታቸውን ያጡ ሲሆን ቁጥራቸው በዛ የሚሉት ደግሞ ቀላልና ከባድ የሆነ ጉዳት ደርሶባቸው በጎንደር ሆስፒታል በሕክምና ላይ ይገኛሉ ።

ከእነዚህ መንገደኞች መሃል በተለይ ዘማሪ ምትኩ በከባድ ጉዳት ውስጥ እንደሚገኝ በአደጋው ሰዓት ወዲያው በመድረስ የሞቱትንም ሆነ የቆሰሉትን ወደ ሆስፒታል የወሰደው የማኀበረ ወይንዬው ሰብሳቢ መ/ር ደረጀ ነጋሽ በስልክ ገልጾልኛል ።

የአደጋው አድራሽ በቅጽል ሰሙ ቀይ ሽብር በመባል የሚታወቀው የቻይና ስሪት የሆነው መኪና ሲሆን የአደጋውን መንስኤ ግን የክልሉ ፖሊስ እያጣራ መሆኑንም ደረጀ አክሎ ነግሮኛል ።

አሁን ይህን ማስታወሻ በመጻፍ ላይ ሳለሁ ደረጀ የሟቾች ቁጥር ወደ 4 ከፍ ብሏል ብሎኛል።

እንግዲህ ምን እንላለን ያረፉትን ነፍሳቸውን ይማር ።


Viewing all articles
Browse latest Browse all 15006

Trending Articles