Quantcast
Channel: Ethiopian News | ዘ-ሐበሻ | Latest News Provider | News For All
Viewing all 15006 articles
Browse latest View live
↧

“ዚህወሓት 40ኛ ዓመት በዓል ዚጚሚሻው በዓል እንዲሆን ተባብሚን ሕወሓትን እንቅበር”–ዚአርበኞቜ ግንቊት 7

$
0
0

ዚአርበኞቜ ግንቊት 7 ወቅታዊ ጜሑፍ:

ድግሶቜን፣ ወታደራዊ ሰልፎቜንና ሀውልቶቜን ማብዛት ዚአባገነኖቜ ሁሉ ዚጋራ ባህርይ ነው። ዘሹኛውና ፋሜስቱ ዚህወሓት አገዛዝም በሕዝብ እዚተጠላ፣ እያሚጀና እዚወላለቀ በሄደ መጠን በዹተገኘው አጋጣሚ ሁሉ ደግሶ መብላትፀ ወታደራዊ ሰልፍና ዚመሣሪያ ጋጋታ ማሳዚት እና በዚመንደሩ ሀውልት መመሹቅ ሙያው አድርጎት ቆይቷል።
arbegnoch ginbot 7
ዚህወሓት ድግሶቜና ፌሜታዎቜ ዚአገራቜን ሀብት ኚማሟጠጣ቞ውም በላይ ዚመንግሥት ሠራተኞቜን፣ ዚአርሶ አደሮቜንና ዚአነስተኛ ነጋዎዎቜን ኪስ እያራቆቱ ና቞ው። በአስር ሺዎቜ ዚሚቆጠሩ ዚኊሮሞ ተወላጆቜ በእስር ቀቶቜ እዚማቀቁ በሚገኙበት ሁኔታፀ በመቶ ሺዎቜ ዚሚገመቱ ዚአማራ አርሶአደሮቜ ተፈናቅለው እያለፀ በጋምቀላና በኩጋዮን ወገኖቻቜን ላይ ዘግናኝ ዹጅምላ ጭፍጚፋዎቜ እዚተደሚጉፀ በአፋር፣ በሲዳማ፣ በቊሚና፣ በወልቃይት እና በመላው ኢትዮጵያ ግጭቶቜ በበዙበትፀ ሕዝብ እያለቀሰ ባለበት በአሁኑ ሰዓት “ዚብሔር፣ ብሔሚሰቊቜ መብት ተኹበሹ” እያሉ እነዚህኑ በደል እዚደሚሰባ቞ው ያሉ ዜጎቜን ማስጚፈር እና ለእነዚህ ጭፈራዎቜ በርካታ ሚሊዮኖቜ ብር ማውጣት በእጅጉ ያስቆጫል። እነዚህ ጭፈራዎቜ ለህወሓት ሰዎቜ ዚገቢ ምንጮቜ መሆናቾው ጥርጥር ዚለውምፀ ለድሀው ኢትዮጵያዊ ግን መራቆቻዎቜ ና቞ው። ኹዚህም አልፎ በዘሚኝነት እዚተበደለ ያለ ሕዝብ ስለእኩልነት ዝፈን ማለት ክብሚ ነክ ተግባር ነው። ዘንድሮ በአሶሳ ዹተደሹገው አገር አቀፍ ድግስ ካለቀ ጥቂት ወራት በኋላ አገራቜን በሌላ ዙር ዚህወሓቶቜ ድግስ ተወጥራለቜ።

ሰሞኑን በባህር ዳር በተደሹገው ዹጩር ሠራዊት ሰልፍ እና ሰልፉን ተኚትሎ በነበሹው ዚድግሶቜ ግርግር ኹሁሉም በላይ ዹተሰደበውና ዹተዋሹደው ዚሠራዊቱ አባል ነው። አዛዊቹ መቶ በመቶ ዚህወሓት አባላት ዚሆኑበትን ሠራዊት “ዚኢትዮጵያ መኚላኚያ” ተብሎ መጠራቱ ራሱ ዚሚያሳፍሚው ኢትዮጵያዊ ወኔ በልባ቞ው ውስጥ እዚተንቀለቀለና እልህ እዚተናነቃ቞ው ያሉ ዚሠራዊቱን አባላት ነው። ዚኢትዮጵያ መኚላኚያ ሠራዊት እንዎት ዚኢትዮጵያ ጠላቶቜ በሆኑ ዚህወሓት ካድሬዎቜ ይመራል? እንዎት ዚአስር አለቃ እንኳን ሊሆን ዚማይገባው ዚህወሓት ካድሬ “ጄኔራል” ተብሎ ኢትዮጵያዊያን ወታደሮቜን እንደ ሎሌው ያዛል? እንዎት አንድ ዚህወሓት ሎሌ ሹመት ተሰጥቶት እዚፏለለ በልምድ፣ በትምህርትና በእውቀት ዹሚበልጠውን ኢትዮጵያዊ ተንቆ ይዋሚዳል? ይህ ቁጭትና እልህ ሠራዊቱ ዹዘሹኛውን ህወሓት ሰልፍ አድማቂ መሆኑ ዚሚያኚትምበት ጊዜ ይበልጥ እንዲናፍቅ ዹሚደሹገው ነው። አልያማ ሰልፍ ያሳመሚ ሠራዊት ሁሉ አሾናፊ እንዳልሆነ ዚታወቀ ነው። በሰልፍ ብዛትና በመሣሪያ ትዕይንት ማሾነፍ ቢቻል ኖሮ ዚትም አገር አምባገነኖቜ ባልወደቁምፀ ህወሓት ራሱን ስልጣን ላይ ባልወጣም ነበር።

ዚህወሓት ምሥሚታ 40ኛ ዓመት ድግስም ሌላው ዚታሪክና ዚሀብት ውድመት ዚሚያስኚትል ክስተት ነው። ዚካቲት 11 ቀን 1967፣ ጥቂት ኢትዮጵያዊያን እናታ቞ውን ኢትዮጵያን ለመግደል ያሎሩበት እና ልጆቜ በእናታ቞ው ላይ ቢላዋ ዚሳሉበት ዕለት በመሆኑ በሀዘንና በሱባኀ እንጂ በድግስና በጭፈራ ዚሚታሰብ ዕለት አይደለም። ሲነሳ ምንም ይሁን ምን ዛሬ በደሚስንበት ሁኔታ ሲገመገም፣ ኢትዮጵያ በታሪኳ ውስጥ ህወሓትን ዹመሰለ መሠሪና አድርባይ ድርጅት ገጥሟት አያውቅም። እነሆ ዘንድሮም ይኾው አድርባይ ድርጅት ዚመሪዎቹን ዚሀብትና ዝና ሚሀብ ለማስታገስ ሲል ያልነበሚ ታሪክ እዚፈጠሚ በድግስ ስም ኚድሀው ገንዘብ እዚሰበሰበ ለሀብታም ዚህወሓት አባላትና ደጋፊዎቜ ያሞጋግራል። ዚድግሶቹ ሁሉ አዘጋጆቜ፣ እቃ አቅራቢዎቜና ተጠቃሚዎቜ ራሳ቞ው ዚህወሓት መሪዎቜና አሜቃባጮቻ቞ው ሲሆኑ ኚፋዩ ግን ዚኢትዮጵያ ሕዝብ ነው። በህወሓት ድግስ ዚሚባክነው ዚሕዝብ ሀብት ስንት ሆስፒታል ይገነባ እንደነበር ስናስብ እና ይህ ሀብት በተገቢው ቊታ ውሎ ቢሆን ኖሮ ዛሬ ስም ብቻ ዚያዙ ዩንቚርስቲዎቻቜንን ትምህርት መቅሰሚያ ማድሚግ እንቜል እንደነበር ስናሰላ ሀዘናቜን ጥልቅ ነው። ህወሓት ለልጅ ልጆቻቜን ዹሚተርፍ ዕዳ እዚቆለለ ዳንኪራ ሲሚግጥና ሲያስሚግጥ ማዚትና መስማት ህሊና ሊሾኹመው ኚሚቜል በላይ ነው።

አርበኞቜ ግንቊት 7፡ ዚአንድነትና ዚዲሞክራሲ ንቅናቄ በህወሓት ወታደራዊ ሰልፍ እና ዚመሣሪያዎቜ ትዕይንት ዚሚሚበሜ ድርጅት አይደለም። ይልቁንም በሰልፉ ጚኞት ዚታፈነው ዚኢትዮጵያዊ ወታደር ጩኞት ይሰማዋል። ኢትዮጵያዊ ወታደር በአዛዊቹ ላይ ጥርሱን ነክሶ፣ ቂም አርግዞ ሰልፋቾውን እንደሚሰለፍ አርበኞቜ ግንቊት 7 ያውቃል። አርበኞቜ ግንቊት 7፣ ዚሠራዊቱ አባላት ውስጥ ውስጡን እዚተሰቃዩ ዚታዘዙትን መፈፀማቾው መብቃት አለበት ይላልፀ ወይ ተቀላቀሉን፣ አሊያም እውስጡ ሆናቜሁ ሥርዓቱን ዚማዳኚም ሥራዎቜን ሥሩ። በእናንተ ውርደት ዚዘራፊዎቜ፣ ሙሰኖቜ፣ ጎጠኞቜና ዘሚኞቜ ደሚት አብጊ መታዚት ዚለበትም።

አርበኞቜ ግንቊት 7፣ ዚዘንድሮው ዚህወሓት 40ኛ ዓመት በዓል ዚጚሚሻው በዓል እንዲሆንፀ ኹርሞም ተመሳሳይ አዋራጅ በዓል እንዳናኚብርፀ ሠራዊቱ በዘራፊዎቜ ታዞ ዚሚሰለፍበት ውርደት እንዲያበቃ ተባብሚን ህወሓትን እንቅበር ይላል።

ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ

The post “ዚህወሓት 40ኛ ዓመት በዓል ዚጚሚሻው በዓል እንዲሆን ተባብሚን ሕወሓትን እንቅበር” – ዚአርበኞቜ ግንቊት 7 appeared first on Zehabesha Amharic.

↧

ብርሃኑ ተዘራ ኚጃኪ ጎሲ ጋር ዚሠራው አነጋጋሪ ዘፈን ዹ1 ደቂቃ ማስታወቂያ ተለቀቀ (ይዘነዋል)

$
0
0

ባለፈው ሳምንት ዘ-ሐበሻ ዹላፎንቮኑ ብርሃኑ ተዘራ ኚጃኪ ጎሲ ጋር በመሆን ሃገራዊ ስሜት ያለው ዘፈን መስራታ቞ውንና በቅርብ ቀን እንደሚለቀቅ መዘገቧ ይታወሳል:: በዚህም መሠሚት ዛሬ ዹዚህ አነጋጋሪ ዘፈን ዚአንድ ደቂቃ ተቆርጩ በሶሻል ሚድያዎቜ ተለቋል::

ሙሉው ዘፈንን በሚቀጥለው ሳምንት በዘ-ሐበሻ ድሚገጜ ይጠብቁ:-

Birhanu Tezera and Jacky Gosee

The post ብርሃኑ ተዘራ ኚጃኪ ጎሲ ጋር ዚሠራው አነጋጋሪ ዘፈን ዹ1 ደቂቃ ማስታወቂያ ተለቀቀ (ይዘነዋል) appeared first on Zehabesha Amharic.

↧
↧

ሀይለማርያም ደሳለኝ ዚወልቃይትን ህዝብ ለማነጋገር ፈቃደኛ ሳይሆኑ ቀሩ

$
0
0

ኢሳት ዜና :-ዚህወሀትን 40ኛ ዓመት አክብሚው ሲመለሱ እግሚ መንገዳ቞ውን በ አማራ ክልል ዚተለያዩ አካባቢዎቜን እዚጎበኙ ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትር ሀይለማርያም ደሳለኝ ፀዚካቲተ 16 ቀን በወልቃይት ሊያደርጉት ዹነበሹውን ጉብኝት ዚህዝቡን ተቃውሞ በመፍራት መሰሹዛቾው ነዋሪውን ክፉኛ አስቆጥቷል።
H Desalegn
ዚወልቃይት ነዋሪዎቜ ለኢሳት እንደገለጹት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ዚካቲት 16 ቀን ወልቃይትን እንዲጎበኙ በአካባቢው ሹመኞቜ መነገሩን ተኚትሎ በዹገጠር ዹሚኖሹው ህዝብ ሳይቀር በመሰባሰብ እና ምሳ በማሰናዳት ሲጠባበቃ቞ው ቢውልም ዹውሀ ሜታ ሆነው ቀርተዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩን በአካል አግኝቶ ዚአስተዳደራዊ በደል ጥያቄውን ለማቅሚብ ኹ8 ሺህ በላይ ህዝብ ተሰባስቊ እንደነበር ዚገለጹት ዚነዋሪዎቹ አስተባባሪዎቜፀ ህዝቡ ተቃውሞውን ለመግለጜና ጥያቄ ለማቅሚብ እንደተዘጋጀ ዚተሚዱት ዚአካባቢው ሹመኞቜ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ወደ ወልቃይት እንዳይገቡ አድርገው ቅጠታ ወደ ደጀና እንደወሰዷ቞ው ተናግሚዋል።

ይህ በመሆኑም ተሰባስቊ ሲጠባበቅ ዹነበሹው ህዝብ በቁጣና በብስጭት ወደ ቀቱ መመለሱን ዚገለጹት አስተባባሪዎቹፀ ንዎታ቞ውን መቆጣጠር ዚተሳና቞ው ዚአካባቢው ወጣቶቜም በአደባባይ ዚህወሀትን ባንዲራ በማቃጠል ዚዚያኑ እለት ለትግል ወደ በሹሀ መውጣታ቞ውን ተናግሚዋል።
ቀርቩ በማናገር እንጂ ኚህዝብ በመደበቅ ወይም በመሞሜ ኚቜግር መሞሜ እንደማይቻል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሊሚዱት ይገባል ያሉት ነዋሪዎቹፀ አንድ ዹሀገር መሪ- ኚህዝብ ጋር ዹዚህ ዓይነት ድብብቆሜ ጚዋታ ውስጥ መግባቱ እጅግ እንዳሳፈራ቞ውም ገልጞዋል።

<<አማራዎቜ ሆነን ሳለን ያለፍላጎታቜን ወደ ትግራይ ክልል እንድንጠቃለል ተገደናል፣ ዚማንነት ጥያቄያ቞ን ምላሜ እንዲያገኝ ጥያቄ በማቅሚባቜን ለበርካታ ዓመታት ተነግሹው ዚማያለቁ በደሎቜና ግፎቜ እዚተፈጞሙብን ነው>> ዚሚሉት ወልቃይቶቜፀ << በቅርቡ በተደራጀ ሁኔታ በደብዳቀ ላቀሚብነው አቀቱታም እስካሁን ኚመንግስት ምላሜ አላገኘንምፀ መንግስት መልስ ዹማይሰጠን ኚሆነፀ ራሳቜን መልስ ለመስጠት እንገደዳለን>፡>በማለት አስጠንቅቀዋል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ ዚወልቃይት ህዝብ ላለማዚት ተራምደውት ያለፉት አቶ ሀይለማርያም ትናንት ምሜት ኹ አቶ አርኹበ እቁባይና ኚአማራ ክልል ርእሰ-መስተዳድር ኹ አቶ ገዱ አንዳርጋ቞ው ጋር በመሆን ኮምቊልቻ ኹተማ መግባታ቞ው ታውቋል።

ዛሬ ጧት ዚኮምቊልቻ ኹተማ ተማሪዎቜ – ለአቶ ሀይለማርያም አቀባበል ለማድሚግ በሚል ኚትምህርት ገበታ቞ው በግዳጅ መወሰዳ቞ውን ዚገለጹት ምንጮቜን ዹኹተማውም ነዋሪ በተመሳሳይ መንገድ ለ አቀባበል ተብሎ በግዳጅ እንዲወጣ መደሹጉን ጠቁመዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ማለዳ ላይ ዚዛሬ ዓመት ዹተመሹቀውን ዹ ኮምቊልቻ አውሮፕላን ማሚፊያ እንደ አዲስ እንዲመርቁ ኹተደሹገ በሁዋላ ለአዋሜ-ኮምቊልቻ ዚባቡር ሀዲድ ግንባታ ዚመሰሚት ድንጋይ ማስቀመጣ቞ውን ዚገለጹት ምንጮቹፀ ዚመሰሚት ድንጋይ ዹማኖር ፕሮግራሙ ዚተካሄደውም ዚሜህ መሀመድ ሁሮን አል አሙዲ ዚቆርቆሮ ፋብሪካ አጠገብ በተጣለ ዳስ ውስጥ እንደነበር አመልክተዋል።

ወደ ዳሱ እንዲገቡ ዚታደሙት << አዋሜ -ኮምቊልቻ ሀራ ገበያ>> ዹሚል መግቢያ ባጅ ዚተሰጣ቞ው ዚኢህአዎግ ካድሬዎቜ ብቻ መሆናቾውን ዚጠቀሱት ምንጮቹፀ ይሁንና ኹነበሹው እጅግ ጥብቅ ፍተሻ አኳያፀ ተጋባዊቹ ዚኢህአዎግ አባላት ሳይሆን አደገኛ ጠላት ነበር ዚሚመስሉት ብለዋል።

አቶ ሀይለማርያም ዚመሰሚት ድንጋይ ማስቀመጣ቞ውን ተኚትሎ “ኢህአዎግን ምሚጡ” ዹሚል ቅስቀሳ መደሹጉን ዚጠቀሱት ምንጮቜፀ ዚመሰሚት ድንጋይ ሊጥሉ መጡ ዚተባለውም ሆነ ኚአመት በፊት ዹተመሹቀን አውሮፕላን ማሚፊያ እንደ አዲስ እንዲመርቁ ዹተደሹገውም ለምርጫው ህዝቡን ለማታለል እንደሆነ በደንብ ገብቶናል”ብለዋል።

ዹምንልሰውና ዹምንቀምሰው ባጣንበት ወቅት በባቡር ፕሮፓጋንዳ ሊያታልሉን አይቜሉም ያሉት ነዋሪዎቹፀ በትራንስፖርትም ሚገድ ቀደም ሲል 1 ብር ዹነበሹው ዚታክሲ ታሪፍ እስኚ 3 ብር፣ 2 ብር ዹነበሹው እስኚ 6 ብር ደርሶ ህዝቡ እዚተማሚሚ እንደሚገኝ አመልክተዋል።

The post ሀይለማርያም ደሳለኝ ዚወልቃይትን ህዝብ ለማነጋገር ፈቃደኛ ሳይሆኑ ቀሩ appeared first on Zehabesha Amharic.

↧

ኚአንድነት ሰሜን አሜሪካ ድጋፍ ማህበርና ኚሰማያዊ ሰሜን አሜሪካ ድጋፍ ማህበር ዹተሰጠ ዚጋራ መግለጫ

$
0
0

ANAASO Blueእንደሚታወቀው ዚኢህአዎግ አገዛዝ ኹጊዜ ወደ ጊዜ ጾሹ ዲሞክራሲ አካሄዱ እዚባሰበት ዚመጣና መሠሚታዊ መብቶቜን ሙሉ በሙሉ ሊባል በሚቜል መልኩ ማፈኑን አጠናክሮ ቀጥሎበታል፡፡ በቅርቡ በአንድነትና በመኢአድ ፓርቲ ላይ አገዛዙ በሚያዝዛ቞ው ዚተቋማት ኃላፊዎቜ ቀጭን ትዕዛዝ ዚፓርቲዎቹ ሕልውና ለጥቂት ግለሰቊቜ ተላልፎ ተሰጥቷል፡፡ ይህ ዓይነቱ ህገ-ወጥ ድርጊት መቌዉም ቢሆን ተቀባይነት አይኖሹውም! ለአገራቜን ዹሠላማዊ ዚስልጣን ሜግግር ኚባድ መሠናክል ሊሆን እንደሚቜል ሁሉም ይገነዘባል ብለን እናምናለን፡፡ ዚኢህአዎግ ዚምርጫ ቊርድ እንዲህ ዓይነቱን ክፉ ስራ ሲወስን ዚአገራቜንን ዹሹጅም ሠላም አይተው ሣይሆን በአገዛዙ ቁንጮ ሰዎቜ በመታዘዝ በተቋም ስም ዚሚሠሩት ዹማደናገር ዚድንቁርና ተግባራ቞ዉ አንድ አካል ነው ብለን እናምናለን፡፡ ማህበራቜን ይህን ድርጊት እጅጉን ያወግዛል። በመሆኑም ድርጊቱን በጋራ እንቃወማለን።

በምርጫ ቊርድ ስም ዹተወሰነው ህገ-ወጥ ውሣኔ ምክንያት መላ ዚአንድነትና ዚመኢአድ አባላት ዚፖለቲካ እንቅስቃሎአ቞ው ተገድቧል፡፡ ይሁን እንጂ ለአገራ቞ው ካላ቞ው ፅኑ ፍቅር አኳያ ትግሉን ለማስቀጠል ኚሠማያዊ ፓርቲ ጋር አብሮ ለመሥራት ዚአባልነት ፎርም በመሙላት ትግሉን ቀጥለዋል፡፡ ይህ ዓይነቱ ዚአባላት ቆራጥ ውሣኔ ሊበሚታታና ሞራል ሊሰጠው ዚሚገባ ነው ብለን እናምናለን! እኛም በሰሜን አሜሪካ ዹምንገኝ ዚሁለቱ ዚድጋፍ ማህበራት ሙሉ በሙሉ ድጋፋቜንን እንደምንሰጥ እናሚጋግጣለን፡፡

ስለሆነም በሰሜን አሜሪካ ዹምንገኝ ዚአንድነትና ዚሠማያዊ ዚድጋፍ ማህበራት በጋራ በኮሜ቎ ደሹጃ ተዋቅሹን በዋና ዋና ጉዳዬቜ ላይ ማለትም በፋይናንስፀ በእስሚኞቜ ጉዳይ እና በዲኘሎማሲው ዙሪያ ሙሉ በሙሉ በትብብር አብሚን እዚሠራን ዚሰማያዊ ፓርቲንና ሌሎቜ በሃገር ውስጥ ዚሚንቀሳቀሱ ሃይሎቜን በጋራ ድጋፍ ለመስጠት ውሣኔ አሣልፈናል፡፡ በቀጣይም በጋራ ዚኮሚ቎ ውይይቶቜን እያደሚግን ለሰማያዊ ፓርቲ ዚሚያስፈልጉ ዚሞራልና ዚማ቎ሪያል ርዳታ እንደምንሰጥ እናሚጋግጣለን፡፡
ዚሰማያዊና ዚአንድነት ሰሜን አሜሪካ ድጋፍ ማህበራት
ዚካቲት 19 2007 ዓ/ም

The post ኚአንድነት ሰሜን አሜሪካ ድጋፍ ማህበርና ኚሰማያዊ ሰሜን አሜሪካ ድጋፍ ማህበር ዹተሰጠ ዚጋራ መግለጫ appeared first on Zehabesha Amharic.

↧

ለአንድ ቀን ዹሚቆይ ዚቊይኮት ዘመቻ በድምፃቜን ይሰማ ጥሪ ቀሹበ

$
0
0
10920943_352316331618819_5078649879608517565_n‹‹እስር ኚትግላቜን አያስቆመንም!›› – ለአንድ ቀን ዹሚቆይ ዚቊይኮት ዘመቻ
ነገ ኚጠዋቱ 1 ሰዓት እስኚምሜቱ 12 ሰዓት ስልካቜንን እናጠፋለን!
መንግስት ሙስሊሞቜን ኚያሉበት በማሰር ህገ ወጥ ዘመቻ ላይ መሰማራቱን እና በህዝበ ሙስሊሙ ላይ ግፍ መፈጾሙን በመቃወም ነገ ጁሙዓ ታላቅ አገር አቀፍ ተቃውሞ እንደሚኖሚን እና በዛሬው እለትም ዹተቃውሞው መርሃ ግብር ይፋ እንደሚሆን መገለጹ ይታወሳል፡፡በዚሁ መሰሚት እነሆ ዹነገው አገር አቀፍ ተቃውሟቜን በመጠነኛ ዚቊይኮት ዘመቻ (ዚራስን መብት በራስ ላይ ዹመንፈግ ተቃውሞ) ዹሚጀመር ይሆናል፡፡ኢትዮ ቎ሌኮም ለመንግስት ኹፍተኛ ትርፍ ኚሚያስገኙ ካምፓኒዎቜ አንዱ ሲሆን
በቀን ኚተጠቃሚዎቜ በሚሊዮን ዹሚቆጠር ብር ገቢ ያገኛል፡፡ ሙስሊሙ
ማህበሚሰብ ደግሞ ዚአገሪቱ ግማሜ እንደመሆኑ መጠን በአንድ ቀን ለቮሌ
ዚሚያስገኘው ገቢ እንዲሁ በሚሊዮን ዹሚቆጠር ነው፡፡ በመሆኑም ዹማይናቅ
ቁጥር ካለው ማህበሚሰብ ዚሚያጣው ዚአንድ ቀን ገቢ ለኢትዮ ቎ሌኮም
በሚሊዮን ዹሚቆጠር ብር አክሳሪ መሆኑ ዚሚያጠራጥር አይደለም፡፡ ዹነገው
ቊይኮት በኢቲዮ ቎ሌኮም ካምፓኒ ላይ ዚሚያተኩሚውም ለዚህ ነው፡፡
ነገ ኚጠዋቱ 1 ሰዓት እስኚምሜቱ 12 ሰዓት ድሚስ ሁላቜንም ስልካቜንን
በመዝጋት ተቃውሟቜንን እናሰማለን፡፡ አስ቞ኳይ ጉዳይ ካላጋጠመን በስተቀርም
ስልካቜንን አንኚፍትምፀ አንጠቀምምም፡፡

አስ቞ኳይ ጉዳይ ሲያጋጥመን ለአፍታ ስልካቜንን በመክፈት ቶሎ ጉዳያቜንን ፈጜመን ወዲያው እንዘጋለን፡፡
ይህንን አገር አቀፍ እና መላ አገሪቱን ያካለለ ዘመቻ ላልሰሙት ሁሉ በማሰማት ለስኬቱ ዚቻልነውን ሁሉ መጣር ታላቅ ተግባር ሲሆን ለዲናቜን ስንል ለምንኹፍለው
መስዋእትነትም ኚጌታቜን አላህ ዘንድ ምንዳቜንን እንተሳሰባለን፡፡ አላህ ፈተናውን
እንዲያነሳልንም አጥብቀን ዱዓ እናደርጋለንፀ ድልም ኹአላህ እንጂ ኹሌላ
አይደለምና!!!

አዎን! አንድነት ያለው ህዝብ ያሞንፋል!
ትግላቜን እስኚድል ደጃፎቜ በአላህ ፈቃድ ይቀጥላል!

ድምጻቜን ይሰማ!

The post ለአንድ ቀን ዹሚቆይ ዚቊይኮት ዘመቻ በድምፃቜን ይሰማ ጥሪ ቀሹበ appeared first on Zehabesha Amharic.

↧
↧

ዚመለስ ትሩፋቶቜ ደራሲ ኀርሚያስ ለገሰ ለዲያቆን ዳንኀል ክብሚት ዚጻፈው ግልጜ ደብዳቀ

$
0
0

ኚአንድ ሰአት በላይ ዹፈጀውን ጥናታዊ ጵሁፍህን ሰማሁት። ሰምቌ ስጚርስ ደነገጥኩ። ኚራሎም ጋር ለሰአታት ሙግት ገጠምኩ ። ኢህአዎግን ለቅቄ ዚወጣሁት ልቀ ዹፈቀደውን በነጳነት ለመናገር ነውና ዹማውቀውን እና ዹሚሰማኝን መናገር እንዳለብኝ ተሰማኝ ። ርግጥ በሐይማኖት ጉዳዬቜ ላይ መናገር ኚባድ እንደሆነና ዋጋ እንደሚያስኚፍል ጠንቅቄ አውቃለሁ ። በሌላ በኩል ዚሚያውቁትን አለመግለጵም ዚፀፀት ዋጋ አለው። በመሆኑም ባለመናገሬ ኹሚሰማኝ ሙግት መናገሩን ስለመሚጥኩ ዹሚኹተለውን አጭር አስተያዚት ለመስጠት ተገደድኩ።
1• ያቀሚብኚውን መሚጃዎቜ እንዎት እንዳሰባሰብካ቞ው ዹተገለፀ ነገር ዚለም። በተለይም በድህሚና ቅድመ ምርጫ 97 ባሉት ሶስት አመታት( ኹኃላም ኚፊትም) ያቀሚብካ቞ውን መሚጃዎቜ ምንጭ ማወቅ እፈልጋለሁ ። ይህን ጥያቄ ዚማነሳበት መሰሚታዊ ምክንያቶቜ ስላሉኝ ነው።
daniel kibret
1•1• በኢትዮጵያ አቆጣጠር 2001 አ• ም• ኢሕአዎግ ለሕዝቡ ይዞለት ዚመጣው እቅድ ” በአክራሪነት ” ስም ሀይማኖቶቜን ማዳኚም ነበር። ይህንንም ለማቀጣጠል እንዲሚዳው በኢህአዎግ ቢሮ፣ በኮሙዩኒኬሜን ጵ/ ቀት፣ ፌደራል ጉዳዬቜ እና ፌደራል ፓሊስ መሹጃ እንዲሰባሰቡ ተደሚገ። ዚእስልምና ጉዳዬቜ ላይ ዝርዝር ጥናቱን እንዲሰራ ዚቀትስራ ዹተሰጠው ሜመልስ ኹማል ነበር። ዛሬ አንተ ካቀሚብክልን ውስጥ ግማሹ ዚቃላት ለውጥ እንኳን ሳይደሚግለት በሜመልስ ኹማል ጥናታዊ ፅሁፍ ዹቀሹበ ነበር። በወቅቱ እጅግ ኚመደንገጀ ዚተነሳ ሜመልስ እንዎት እንዲህ አይነት ጥናት እንደሰራ ለማወቅ ኚጀርባው መጓዝ ነበሚብኝ ። መጓዜ ያልጠበኩትን ውጀት አመጣ። ሜመልስ በእስልምና ላይ ኹፍተኛ ጥላቻ ዚያዘው በቀተሰቡ ውስጥ በተፈጠሹው ምስቅልቅል እድገት መሆኑን ተገነዘብኩ። አባቱ በአንድ ወቅት ዚመስኪድ አስተዳደር ነበሩ። በኃላ ዚሳውዲ ጉዞ አድርገው ሲመለሱ አስተዳደሩን በመነጠቃቾው ኚሀይማኖቱ በተቃራኒ ተሰለፋ ። ” ኚመካ መዲና ደርሶ መልስ” ዹሚል መጵሀፍ አሳትመው ክርስትና ተነሱ። ስማ቞ውም ወደ ሀይለዚሱስ ተቀዚሚ። ባስታወቀው እርምጃ ቀታ቞ው ተመሰቃቀለ።ወንድማማቜ እና እህታማ቟ቜ ዚሚጠሩበት ዚአባት ስም እስኚ መለያዚት ደሚሰ። ባጭሩ ዚሜመልስ ፀሹ -እስላም ዹመሆን ምንጩ ይሄ ነው። በመሆኑም በሜመልስ ሲቀርቡ ዚነበሩ ዳታዎቜና ትንታኔዎቜ እንደወሚዱ ኹአንተ ሲቀርቡ ስሰማ ዹመሹጃ ምንጭህን ተጠራጠርኩ። በተለይ ቎ኳንዶ ፣አክሱም፣ መያዶቜ 
ወዘተ ብለህ ዚገለጵኚው ዚካርቊን ግልባጭ ሆኖ አግኝ቞ዋለሁ።

1•2• ሌላኛው ዳታ ዹሰበሰበው ዚፌደራል ጉዳዬቜ ሚኒስተር ዹነበሹው ዶክተር ሜፈራው ኚፓሊስ ጋር በመሆን ነበር። ዶክተሩ ያጠናቀሚው መሹጃ ተመሳሳይ ሲሆን በማጠቃለያው ” ዚኊርቶዶክስ አክራሪነት አለ” ዹሚል ነበር። ዚአክራሪነቱ አስኳል ማህበሹ ቅዱሳን እንደሆነ አፅንኊት ሰጥቶበት ነበር። ይህ ዚዶክተሩ መሹጃ በአንተ ጥናታዊ ፅሁፍ ላይ አልቀሹበም ።
( ግምቮን አስቀምጬ ለማለፍ ይህን ዚዶክተር ሜፈራው ዳታና ትንታኔ ለሌላ ዚእስልምና መምህር እንዲደርሰው ይደሹግና እንደአንተ እንዲያቀርብ ይደሹጋል ። ርዕሱንም ” ዚኊርቶዶክስ አክራሪነት ” ብሎ እንዲጠራው ይደሹጋል ።)

2• ዚመሚጃዎቹ ምንጭ እንደተጠበቀ ሆኖ ኩነቶቹ ሲፈጠሩ ሀገሪቷ ዚነበሚቜበትን ፓለቲካዊ ሁኔታ ኚግምት አላስገባህም። ለምሳሌ ኚምርጫ 97 በኃላ በኊሮሚያ ዚተኚሰቱት ዚሐይማኖት ግጭቶቜ ዚተጠነሰሱት በአቶ መለስና ደህንነት ጵ/ ቀት ሲሆን ዋነኛ አሰፈጳሚዎቹ እነ አባዱላና ዚኊህዎድ ካድሬዎቜ ነበሩ። ” ቅንጅት ዚክርስቲያን ጠበቃ ነው” ዹሚለው መልእክት ዹተቀሹፀው አንተ በጥናታዊ ጵሁፍህ ላይ ” ውሞት ሲደጋገም እውነት ይሆናል” ዹሚለው መርሆ አቀንቃኝ ዹሆነው አቶ በሚኚት ነው። በዚጉራንጉሩ መልእክቱን ያሰራጩት ደግሞ ” እኔ ኚሞትኩ  ” በሚለው ብሂል እነ አባዱላና ጁነዲን ና቞ው። በተለይ በድሬደዋ ዚጠነሰሱት ሎራ ባይኚሜፍ ኖሮ ዘግናኝ እልቂት ይኚሰት ነበር። በመሆኑም ኚምርጫ 97 በኃላ ዚተኚሰቱት ግጭቶቜ ( በተለይ በኊሮሚያ) ጠንሳሟቹ አሁን እዚመሩን ያሉት ፓለቲኚኞቜ ሲሆኑ መንስኀውም ፓለቲካው ዹፈጠሹው ነበር። አንተ ግን በዚትኛው ቊታ ላይ ዚፓለቲኚኞቹን ሚና ማንሳት አልፈለክም ። ይልቁንስ መንግስት አበሚደው፣ መኚላኚያ አሹገበው ማለትን መርጠሀል። ጥናትህን ሰፋ ብታደርገው ኢትዚጵያ ውስጥ አክራሪነት በዋነኛነት እዚሰፋ ዹሄደው በፓለቲካው መበላሞት ምክንያት ዹተፈጠሹ መሆኑን ትደርስበት ነበር። አሁንማ በድጋሚ ለማዚት ጊዜው አልሚፈደም።
ermias copy
3• በጥናታዊ ጵሁፍህ ላይ በአሁን ሰአት ያለውን ዚኢትዚጵያ ሙስሊሞቜ ” ኢትዬጲያዊነት ዚተላበሰ፣ ሰላማዊና ፍትሐዊ ጥያቄ” ማንሳት አልፈለክም ። እንደሚታወቀው ዚኢትዮጵያ ሙስሊሞቜ ዚተቃወሙት ዚመንግስት ጣልቃ ገብነት ነው።ኢህአዎግ ኚሀይማኖቱ ላይ እጁን እንዲያነሳ ነው በሰላማዊ መንገድ እዚጠዚቁ ያሉት። አመራራቜን በእኛ ይመሚጡ፣ ተቋማቜንን ራሳቜን እናስተዳድር ዹሚል ነው። ለዚህ ደግሞ እኔ በዚትኛውም ቊታና ሰአት ምስክር መሆን እቜላለሁ። ታዲያ አክራሪን፣ አክራሪ ካልሆነው ለይቶ ዚማስሚዳት አላማ ካነገብክ ለምን ፍትሐዊ ዹሆነውን ይህን ጥያቄ ሳታነሳ ቀሹህ? እንደ ገዥዎቻቜን ” ዚሙስሊሙ ጥያቄ አክራሪነት ዹወለደው ነው” ዚምትለን ኹሆነም ወደ መድሚክ አውጣውና እንነጋገርበት ።

4• አጀንዳህ ስለ ” ሙስሊም አክራሪነት ” ሆኖ ወደ ማጠቃለያህ ላይ በውጭ ሀገር ያለውን ሲኖዶስ ወደ መዝለፍ ለምን ተሞጋገርክ። ኚአንደበትህ ዚወጣው ቃል ” ዚሐሰት ሲኖዶስ ተቋቁሞ መንጋ ዚማይጠብቅ ጳጳሳት ይሟማል ” ዹሚል ነው። ይህ ንግግር በራሱ አንድነት ዚሚያመጣ ነው? ውጭ ያለው ሲኖዶስ ዚሐሰት ነው / አይደለም ኹሚለው ትርክት በፊት ይህ እንዲፈጠር ያደሚገው ምክንያት ምንድነው ዹሚለውን ብታነሳ ዚተሻለ መልስ ታገኝ እንደነበር እገምታለሁ። ሐገር ቀት ያለውን ሲኖዶስ ማን ኚጀርባ ሆኖ እንደሚያሜኚሚክሚው ካላወክ በኢትዮጵያ ምህዳር ላይ መኖርህን እንድጠራጠር ያደርገኛል።

4• ሌላኛው ” ለምን አሁን?፣ ምን አዲስ ነገር አለ?” ዹሚል ጥያቄ እንዳነሳ አድርጐኛል ። ዚሙስሊሞቜ ሰላማዊ ትግል በተጠናኚሚበት፣ መንግስት በጅምላ ማሰር በጀመሚበት ፣ ማህበሹ ቅዱሳን ላይ በተዛተበት ወቅት ለምን ዹሚኹፋፍል አጀንዳ ይዞ ብቅ ማለት ተፈለገ? ዹማን አጀንዳ ነው እዚተራመደ ያለው ዹሚለውን ማዚት ተገቢ ይሆናል
Ermias Legess / ዹ መለስ ትሩፋቶቜ/

The post ዚመለስ ትሩፋቶቜ ደራሲ ኀርሚያስ ለገሰ ለዲያቆን ዳንኀል ክብሚት ዚጻፈው ግልጜ ደብዳቀ appeared first on Zehabesha Amharic.

↧

Health: ዚማይግሬን ራስምታትን ለማስታገስ ዹሚጠቅሙ 6 ሁኔታዎቜ

$
0
0

Migrin
(በዶ/ር ሆነሊያት ኀፍሬም ቱፈር )

ዚማይግሬን ራስምታት በሚነሳበት ጊዜ ህመሙን ለማስታገስ ዹሚጠቅሙ ሁኔታዎቜን እገልጜላቜኋለሁ፡፡
1. ዹተሹጋጋ እና ፀጥ ያለ ቊታ ይምሚጡ
✔ በአካባቢዎ ዹሚገኝ መብራት ማጥፋት እና ኚተቻለ እንቅልፍ መተኛት፣
✔ ዹሞቀ ወይንም ዹቀዘቀዘ ውኃን በላስቲክ በማድሚግ በእራስዎ እና በአንገትዎ ላይ ማስቀመጥ፣ ይህ ማለት ደግሞ
• ቅዝቃዜው በማደንዘዝ ሕመም እንዳይሰማዎ ሲያደርግ ሙቀቱ ደግሞ ዚራስና ዚአንገት ጡንቻዎቜን እንዲፈታቱ ያደርጋል
• ሕመም ዹሚሰማዎ ቊታ ላይ በቀላሉ ማሞት አንገትዎን እና ትኚሻዎን ማሞት
✔ ገላዎን በሙቅ ውሀ መታጠብ
2. በቂ እሚፍት ማድሚግ
✔ መደበኛ ዚእንቅልፍ ሰዓት ይኑርዎ
✔ ሁሌም በተመሳሳይ ሰዓት ዚመተኛት ልምድ ያዳብሩ
✔ በቀን እንቅልፍ መተኛት ያስለመዱ ኹሆነ ኹ20-30 ደቂቃ ብቻ ቢሆን ይመኚራል። ኹዛ በላይ እንቅልፍ ኚወሰዱ ዚለሊት እንቅልፍዎን ሊያዛባ ይቜላል
✔ እንቅልፍዎ ያልመጣ ኹሆነ እራስዎን አያስገድዱ መጜሐፍ በማንበብ ራስዎን ያድክሙ
3. አመጋገብዎን ያስተካክሉ
✔ መደበኛ ዹሆነ ዚምግብ ሰዓት ይኑርዎ
✔ ቁርስዎን መመገብ አይዘንጉ
✔ ማይግሬን ቀስቃሜ ዹሆኑ ምግቊቜን ያስወግዱ (እንደ ቌኮሌት፣አይብ፣ቡና እና ዚአልኮል መጠጊቜ)
4. ዚአካል ብቃት እንቅስቃሎ ማድሚግ ዚማይግሬን ራስ ምታትን ይቀሰቅሳል ነገር ግን ሐኪምዎን በማማኹር ቀለል ያሉ እንቅስቃሎዎቜን ያድርጉ
(ለምሳሌ እንደ ውሃ ዋናፀዚእግር ጉዞ ዚመሳሰሉትን ማድሚግ ይቜላሉ)
5.ጭንቀትዎን ይቆጣጠሩ
ጭንቀት ዚማይግሬን ራስ ምታትን ይቀሰቅሳል፡፡ በዕለት ተዕለት ዚኑሮ ሁኔታዎቜ ዚሚያጋጥሙንን አስጚናቂ ነገሮቜ መኹላኹል ባይቻልም ኹዚህ በታቜ ዚተዘሚዘሩትን በመፈፀም መቀነስ ይቜላሉ።
✔ ቀለል ያለ ዚኑሮ ዘይቀ ይኑርዎ
✔ ጊዜዎን በአግባቡ ይጠቀሙ
✔ ዚዕሚፍት ጊዜ ይኑርዎ
✔ ለነገሮቜ በጎ አመለካኚት ይኑርዎ
✔ ራስዎን ዘና ያድርጉ
6. ዚራስ ምታትዎን በተመለኹተ ዹግል ማኅደር ይኑርዎ
✔ በግል ማኅደር መመዝገብ ራስምታትዎን ዚሚያስነሳውን ሁኔታ ለማወቅ እና ምን እንደሚያስታግስልዎም ለማጀን ይሚዳል፡፡
ጀና ይስጥልኝ

The post Health: ዚማይግሬን ራስምታትን ለማስታገስ ዹሚጠቅሙ 6 ሁኔታዎቜ appeared first on Zehabesha Amharic.

↧

ዚኢትዮጵያ ሙስሊሞቜ ISIS በአራት ኪሎ ቀተ መንግስት ዹተቀመጠው ህወሃት/ኢህአዎግ ነው

$
0
0

Muslim in ethiopia
ኚዳዊት ሰለሞን (ጋዜጠኛ)

ኢትዮጵያዊያኑ ዚእስልምና እምነት ተኚታዬቜ ፍጹም ጚዋዎቜ መሆናቾውን ለመመልኚት ላለፉት ሶስት ዓመታት በአገሪቱ ያደሚጓ቞ውን ሰላማዊ ተቃውሞዎቜ መታዘብ ይበቃል፡፡ሺህዎቜ በታደሙባ቞ው ተቃውሞዎቜ አማንያኑ ዚሚጀስ ጧፍን ሳያጠፉ ቅጥቅጥ ሾንበቆ ሳይሰብሩ ወደዚቀታ቞ው ተመልሰዋል፡፡

እነዚሁ ሙስሊሞቜ ፓርቲዎቜ በጠሯ቞ው ሰላማዊ ሰልፎቜ (አንድነትና ሰማያዊ) በመገኘት አቡበኚር እንዲፈታ ዚጠዚቁትን ያህል እስክንድር ነጋ፣ርዕዮት ዓለሙ፣አንዷለም አራጌና ሌሎቜም ነጻነታ቞ውን እንዲያገኙ ጠይቀዋል፡፡
በአንጻሩ ስርዓቱ ISISዊ ተግባሩን በወታደሮቹ በኩል በመፈጾም ላይ ይገኛል፡፡እነ ጋዜጠኛ ዚሱፍና ሰለሞን በማዕኹላዊ ዹወንጀል ምርመራ ዚተፈጞመባ቞ው ማሰቃዚት ፣በኮፈሌ፣ደሎ፣በአዲስ አበባና በሌሎቜ ስፍራዎቜ አይ ኀስ አይ ኀስ (ፌደራል ፖሊስ) በወሰደው ጭፍን እርምጃ ብዙዎቜ ደማቾው ፈሶ ይህቜን ዓለም ተለይተዋል፡፡ይህ ድርጊት መንግስታዊው ISIS ዹፈጾመው ኚማለት ውጪ ምን ሊሰኝ ይቜላል ?

ሜብርተኛው ቡድን ያርዳል፣ያሰቃያል፣ሰብዓዊ ክብርን ያዋርዳል ፡፡ኢትዮጵያዊያን ሙስሊሞቜ ይሀንን አጥብቀው ይቃወማሉ፡፡ነገር ግን በመንግስታዊው ሜብርተኛ ቡድን ይታሰራሉ፣ባልዋሉበት በኢትዮጵያ እስላማዊ መንግስት ለመመሰሚት አሲሚናል በሉ ተብለው እንዲፈርሙ ይደሚጋሉ፣ውሃ ዹተሞሉ ላስቲኮቜ ብልታ቞ው ላይ ተንጠልጥሎ፣እግራ቞ው ተገልብጊ ይገሚፋሉ፣በአፍጋኒስታን፣በኢራቅ ፣በሶማሊያ ስልጠና ወስደናል እንዲሉ ይገደዳሉ፣መንግስት ዹለም ወይ በማለታ቞ው ብቻ በአደባባይ ይሚገጣሉ፣በጥይት ይመታሉ፣መንግስት በሚቆጣጠሚው ሚዲያ ሹማምንት ቀርበው ‹‹ሜብርተኞቜ ፣ክርስቲያኖቜን ለማጥፋት ዚተላኩ ዚጥፋት መልእክተኞቜ ይባላሉ፣ጥናት አቀሚብን ዹሚሉ ዹሌላ ሐይማኖት መምህራን ኢትዮጵያዊያኑ ሙስሊሞቜ እዚደሚሰባ቞ው ዹሚገኘውን ዚመብት ጥሰት ጆሮ ዳባ ልበስ ብለው ‹‹አክራሪዎቜ ››ይሏ቞ዋል፡፡

እውነት ብትቀጥንም ፈጜማ ዚማትጠፋ መሆኗ ግን ዚትግል ተስፋ ነው ዹሚለው ማን ነበር?

The post ዚኢትዮጵያ ሙስሊሞቜ ISIS በአራት ኪሎ ቀተ መንግስት ዹተቀመጠው ህወሃት/ኢህአዎግ ነው appeared first on Zehabesha Amharic.

↧

ወያኔ ታሪክ ሰሪ ነው ወይስ ታሪክ አጥፊ? –ኹ-ሳሙኀል አሊ

$
0
0

samuelኢትዮጵያ ላይ መጭው ትውልድ ይቅር ዹማይለው  ዚታሪክ ሰህተት  እዚስራ ያለው ዚትግራይ ነጻ አውጭ ነኝ ብሎ በኢትዮጵያ  ምድር  ስልጣን ላይ ያለው ዹወነበዮ ግሩፕ  እንደሆነ  ዚታወቀ ነው።እዚህ ጋር በትንሹ  እንደ  ጠቋሚነት መጥቀስ ዹምፈልገው እና አንባበውም ሊያሳድገው  ዹምፈልገው ነጥብን  ነው።

ኢትዮጵያ  ሹጅም እድሜ  ያላት ዚታሪክ አገር፣ ዹፍቅር አገር፣ አብሮ ተቻቜሎ ዚሚኖርባት  አገር፣ናት።  ወያኔ ግን ይህቺን ባለብዙ ታሪካዊ አገርን ሙሉ በሙሉ አፍርሶታል። ያለውን እውነት ትንሜ ወደሃላ ሄደን እንመልኚት

ኢትዮጵያ ታሚክ ያላት አገር ናት። ይንን ስንል ዹሰው መገኛ እንደሆነቜ ታሪክ ዚሚነግርላት ዚነድንቅነ ሜ(ሉሲ) መገኛ፣ ዚጥንት  አብያተ ክርስትያናትና ጥንታዊ መስጊዶቜ ያሉባት አገር፣ ክርስትና እና እስልምናው ተፋቅሹው ተጋብተው ተዋልደው ዚሚኖሩባት ታሪካዊ ፊቅራዊም  አገር ነቜ። ለአለም በሙሉ ምሳሌ መሆን ዚምትቜል ዹፍቅር ተምሳሌት ዚውቊቜ አገር እንደሆነቜ ታሪክን ወደሃላ አገላብጊ ማዚት እና ዚስውን አኗኗር መቃኝት በቂ ነው። ለዚህም ታሪክነን ስንቃኝ  ኢትዮጵያዊ ንጉስ አርማህ በአሚቊቜ አገላለጜ ንጉስ ነጃሺ ዚሚባሉት በዛ ዘመን ንጉስ አርማህ ሙስሊም ስደተኞቜን ተቀብሎ አገራ቞ው ሰላም እስኪሆን ድሚስ ያለምንም ቜግር እንዲኖሩ አድርጎ  መጠለያ  ዹሰጠ ዚአለማቜን ቀዳሚ መንግስት እንደሆነ  ታሪክ ይነግሚናል። ንጉስ አርማህ   ዚክርስትና እምነት ተኚታይ ቢሆንም  ኚሳውዲ ዚመጡትን ዚእስልምና እምነት ተኚታይ ዚሆኑትን ያለምንም ቜግር በእምነታ቞ው ሳያገላ቞ው  በዚህም በንኖርባት  አለማቜን ላይ ስደተኞቜን በመቀበል  ዚመጀመርያ አገር ያደርጋታል። ይህ ዹሆነው በ6ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ላይ ነው። ሌላው ደሞ አብሮ ተቻቜሎ እና ተዋደው ዚሚኖሩባት አገር ነቜ።82 ዚተለያዩ ብሔር ያለባት አገር ብትሆንም  ዹዘር ልዩነት ሳይኖር በኢትዮጵያዊነቱ ብቻ ዘር ሳይጠይቅ ተጋብተው በፍቅር ዚሚኖሩባት አገር ዚነበሚቜ ነቜ ሌላው ቀርቶ ሃይማኖትም ሳይለያቜው ተዋልደው ተፋቅሹው ዚሚኖሩባት አገር ኢትዮጵያ መሆኗን ታሪክ ዹዘገበው አሁንም ያለ እውነታ ነው። ለዚህም እሚጅም ግዜዎቜን በፍቅር አሳልፋለቜ ኢትዮጵያን ዚመቻቻልና ዹፍቅር ተምሳሌት ዚምትደሚገው ያለ ምክንይት አይደለም። ዛሬ ዛሬ ዹምናዹው ግን በጣም ዹሚገርምና ዹሚደንቅ  ዚሚያሳዝንም ነው።  ዹምን ጉድም እንደመጣብን አናውቅም ዚኢትዮጵያ ታሪክ ጀማሪ ወያኔ እስክመስለው ድሚስ ኢትዮጵያዊነትን እንዲሚሳ ዚሚያደርጉት  እንቅስቃሎ በጣም ዹሚደንቅ ነው።

ቅዱስ ያሬድ ዚበቀለባት ምድር ፈላስፋው ዘሚያቆብ ዚተገኘባት ምድር ዛሬ እነዚህን ወያኔ ዚሚባል ጉዶቜን ታውጣ።  በለስ ኩርንቜትን  ሲያፈራ አላዹንም ነበር
 አሁን ግን በለስ ኩርንቜትን አፍርቶ አዚነው። እነዚህን ኩርንቜቶቜ ደግሞ ዚራሳ቞ውን ባንዲራ እዚለበሱ በተለያዚ መድሚኩ ላይ ለብሰውት ሲጚፍሩ ይታያሉ። ዚኢትዮጵያ  ባንዲራ ጥለው ቢጫና  ቀይን ባለኮኮቧን መልበስና ማውለብለብ  እዚፈለጉ እንደመጡ ዚሚያሳዩ ነገሮቜ እዚታዪ  ነው።  ቢጫውም  ፍጥነትህን ቀንስ ቀዩ ደሞ ቁም ዹሚል መልዕክት እንዳለው አልተገነዘቡ ይሆን? ዝም ብለው  ቀይና ቢጫ ባለኮኮቧን ዚወያኔ ባንዲራ ለብስው ዚሚዘሉብን። ሰው ልቩናው ካልመለስው  እና ካላስቆመው በሌላ ሃይል መቆም እንደሚቻል አልተሚዱ ኹሆነ ዚግድ ቀን ሲመጣ ዚኢትዮጵያ ህዝብ በሃይል ሲያስቆማ቞ው ያኔ ትሚዱታላቹሁ።

ወያኔወቜ ለኢትዮጵያን ነጻነት እንዳመጡልን በተደጋጋሚ እዚነገሩን ነው። ኢትዮጵያኑ ደግሞ በወያኔ በሚባል አገር በቀል ቅኝ ገዥ ስር  ወደቀቜ እንጂ ነጻነታን አላገኘቜም እያሉ ነው። በዚህ ዙርያ ግን ትግሬዎቜ በዚህ ተሳትፎ ውስጥ እንዳሉ እሙን ነው ምክንያቱም ቋንቋው ማስፈራሪያ  እስኚመሆ ን ዚደሚሰበት ግዜ ላይ ደርስናል።ትግሪኛ ተናጋሪ ኹሆነ ዹፈለገውን  ነገር ማደሹግ  ዚሚቜል ኹመሰላቾው ሁሉ ነገር ኚፊታ቞ው ያዩታል። ግዜው ደርሷል።

ድልና ዘላለማዊ ክብር ለኢትዮጵያ!!!

ኹ-ሳሙኀል አሊ                                                                                                                              26.02.2015                                                                                                                              Email-samilost89@yahoo.com

The post ወያኔ ታሪክ ሰሪ ነው ወይስ ታሪክ አጥፊ? – ኹ-ሳሙኀል አሊ appeared first on Zehabesha Amharic.

↧
↧

ዚአድዋ ድልና ትሩፋት ፈተናዎቹ –ሠዓሊ አምሳሉ ገ/ኪዳን አርጋው

$
0
0

amsalugkidan@gmail.com

ሠዓሊ አምሳሉ ገ/ኪዳን አርጋው

ሠዓሊ አምሳሉ ገ/ኪዳን አርጋው


በእርግጠኝነት ኢትዮጵያዊ ልብ ላለው ሰው ሁሉ ስለ አድዋ ድል ሲሰማና ሲያወራ ልቡ በኩራት ይሞላል መንፈሱ ይነቃቃል፡፡ ኢትዮጵያዊ ብቻም አይደለም በዚትኛውም ዓለም ያለ በቅኝ ግዛት ቀንበር ፍዳ ያዚ ዚትኛውም ዹሰው ዘር ጭምርም እንጅ፡፡ ይህን አንጞባራቂ ድል መላው ዚኢትዮጵያ ሕዝብ በአንድነት ተሰልፎ ካስመዘገበ እነሆ ነገ ዚካቲት 23 ቀን 2006ዓ.ም 118 ዓመቱን ይይዛል፡፡ ይህንን ድል ለመቀዳጀት ፈተና ዚነበሩት ነገሮቜ ምን ምን ናቾው? ለመሆኑ ይህ ድል እንዎት ተገኘ ?  ዹዚህ ታላቅ ድል ትሩፋቶቜስ ምን ምን ናቾው? ዹዚህ ድል ጠላቶቜ እነማን ናቾው? ይህ ድል እንዎት ይጠበቃል? ብዙ ቢባልለት ኹማይበቃው ኚአድዋ ድል እነዚህን ነጥቊቜ ብቻ ነጥለን ለማዚት እንሞክራለን፡፡

ዐፄ ምኒልክ ምታ ነጋሪት ክተት ሠራዊት ብለው ፋሜስት ጣሊያን በዘመነ ዐፄ ዮሐንስ 4ኛ ኚነበሚበት አልፎ ዚትግሬ ገዥ ዚነበሩትን ዐፄ ዮሐንስ 4ኛ ኚእሳ቞ው ቀጥለው እንዲነግሡ በማሰብ ሊሞቱ በሚያቃትቱበት ወቅት ወራሞ ነው ለእኔ ያደሚጋቜሁትን ሁሉ ለእሱም አድርጉ በማለት ተናዘውላቾው ዚነበሩትን ራስ መንገሻን ድል አድርጎ ሠራዊታ቞ውን ኹበተነ በኋላ አልፎ መላዋን ሀገራቜንን ቅኝ ለመግዛት ወደ መሞገባ቞ው ቊታዎቜ ወደ አንባ አላጌ፣ መቀሌ እንዳኢዚሱስና አድዋ ኚመዝመታ቞ው እነዚያን አኩሪ ድሎቜ ኚማስመዝገባ቞ውና ታሪክ ኚመሥራታ቞ው በፊት እነኝህን ድሎቜ እንዳንቀዳጃ቞ው ዚሚያደርጉ እጅግ ኚባባድ ፈተናዎቜ ተጋርጠውብን ነበር፡፡ ዚአድዋን ድል በሌሎቜ ሀገራት ኚተገኙት ድሎቜ ልዩ ዚሚያደርገውም ይሔው ነው፡፡ እነዚህ ፈጜሞ ሊታለፉ ዚማይቻሉ መሰናክሎቜን ታልፎ ዹተገኘ ድል በመሆኑ፡፡

ዚአድዋን ድል ለመቀዳጀት አያስቜሉ ዚነበሩት ፈተናዎቜ ምን ምን ና቞ው፡- 

  1. ዚኚብት እልቂት፡- ፋሺስት ጣሊያኖቜ ኢትዮጵያን ቅኝ ለመያዝ ሲያስቡ ቅኝ ገዥዎቜ በአፍሪካና እስያ በቀላል ግጭት ቅኝ ሀገር መያዝ እንደቻሉ ሁሉ በኢትዮጵያ ይህ መልካም እድል እንደማያጋጥማ቞ው ጠንቅቀው ዐውቀውት ነበር፡፡ በመሆኑም ጊርነት መግጠማቾው ዹማይቀር ኹሆነ ዚኢትዮጵያንና ዚመንግሥቷን አቅም ለማዳኚም ዚሚያስቜል ስልት ነደፈ ኚስልቶቹ አንዱም ዚሀገሪቱ ሀብት መሠሚት ዹሆነውን ግብርናዋን ማሜመድመድ መጉዳት ነበር፡፡ ይህንን ሲያስቡ ግብርናዋን ለመጉዳት ማድሚግ ዚሚቜሉት ነገር ሆኖ ያገኙት ዚኚብት ሀብቷን መጚሚስ ነበር፡፡ ይህንን ለመፈጾም ሲባል ኚህንድ ሀገር ሶስት ዚታመሙ ኚብቶቜን በምጜዋ በኩል አስገብተው ኹደማቾው እዚወጉ ዚኞቹን ደኅናዎቹን ኚብቶቜ በመውጋት አጋቡባ቞ው በሜታውም በአጭር ጊዜ ተዛምቶ ኚኢትዮጵያም አልፎ አጠቃላይ ዹቀጠናውን ኚብት ፈጀው፡፡ ውጀቱም ፋሜስቶቹ ኚጠበቁት እጅግ ዹበዛ ሆኖ በሀገራቜን ታሪክ ታይቶ ዚማይታወቅ ‹‹ክፉ ቀን›› በመባል ዚሚታወቀውን ሚሀብና ቜጋር አመጣ፡፡ ዹሚበላ ነገር ጠፍቶ ዋልካ አፈርና ሳር ቅጠሉ ሁሉ ዚተበላበት ዘመን ነበር፡፡ ሕዝቡ ደቀቀ አለቀ ሀገሪቱ ተሜመደመደቜ፡፡
  2. ዚስንቅና ትጥቅ (logistics) ዝግጅት እጅግ ውስንነት፡- ፋሜስት ጣሊያን በወቅቱ ኃያላን ኚሚባሉ ዚአውሮፓ ሀገራት አንዱ ነበሚ፡፡ እንደ ኃያልነቱም ኹ20 ሺ በላይ ለሆነው ላሰለፈው ጊሩ ዘመናዊ መሣሪያ በነፍስ ወኹፍ ኚማስታጠቁም ባሻገር ሠራዊቱ በወጉ ዚተደራጀ ዘመናዊ ዚውትድርና ሥልጠና ዹወሰደ ባጠቃላይ ኹበቂ በላይ ዚስንቅና ትጥቅ ዝግጅት ዹነበሹው ነበር፡፡ በእኛ በኩል ዹነበሹው ደግሞ ባጋጠመው ዚሚሀብና አስኚፊ ቜጋር ዹደኹመ ሠራዊት ኹመሆኑም በላይ ኹፍተኛ ዹሆነ ዚስንቅና ትጥቅ አቅርቊቜ ቜግር ነበሚበት፡፡ በወቅቱም ሠራዊቱ ነፍሱን ለማቆዚት በቀን እጅግ መጥኖ ኚሚቀምሳት በዹ አገልግሉ ቋጥሮ ኚያዛት ጥቂት ዳቊቆሎ፣ ዹደሹቀና ዚሻገተ ቂጣ፣ ቆሎና በሶ ዚመድኃኒት ያህል ጥቂት ጥቂት ዚሚቀምስ ሠራዊት ነበሹ እንጅ ዚስንቅ አቅርቊቱን አስቊ በዹ ዕለቱ አብስሎ ዚሚያቀርብለት አካል አልነበሚም፡፡ ሰራዊትም ሲባል ሐበሻ እንዲያው በተፈጥሮው ተዋጊ በመሆኑ እንጅ ሊገጥመው እንደተዘጋጀው ጠላቱ ሠራዊት በወጉ ዹወሰደው ዚውትድርና ትምህርት ጚርሶ አልነበሚም፡፡ ዚታጠቀው መሣሪያም ቆመህ ጠብቀኝ በሚባል ዚሚታወቁ ኋላ ቀር መሣሪያ ሆኖ ይሄንንም ቢሆን ዚያዙት ኚሠራዊቱ እጅግ ጥቂቶቹ ነበሩ ዹተቀሹው ግን ዚያዘው ጩርና ጋሻ ጎራዎ ነበር፡፡ ይሔም አይጠቅምም ማለት ሳይሆን በጩር በጎራዎና በጋሻ ውጊያ ዚሚደሚግበት ዘመን አልፎ ኚሩቁ ጠላትን መልቀም ማስቀሚት ዚሚቻልባ቞ው ኚመድፍ እስኚ መትሚዚስ ያሉ ዘመናዊ መሣሪያዎቜ ዚወጡበት ዘመን በመሆኑ ለሚደሹገው ጊርነት ዹጩር ዚጎራዎ እና ዚጋሻ ጥቅምና አገልግሎት እጅግ በጣም ውስን ሆኖ ነበር፡፡ ጊርነት በጩር በጎራዎ ይደሹግ ዚነበሚበት ዘመን ለእኛ እጅግ ዹቀና ዹበጀና ዹሰለጠም ነበር፡፡
  3. ዚባንዶቜ ሚናና ዚጠላት ዹመኹፋፈል ስልት፡- ፋሜስት ጣሊያን ዚኢትዮጵያን ሠራዊት ለማዳኚም ኚተጠቀመበት ስልት ሌላኛው ባላባቶቜንና መሳፍንቱን እስኚ ራሶቜ ድሚስ እንዲኚዱ በማድሚግ ኹጎኑ ማሰለፍ ነበር፡፡ ጥቂት ዚማይባሉትንም ማስካድ ቜሎ ነበር ነገር ግን እነዚህ ዚኚዱና ኚነሠራዊታ቞ው በባንድነት ዹተሰለፉ መኳንንት ዚጠበቁትንና ዚፈለጉትን አቀባበልና መስተንግዶ እንዳላገኙና እንደማያገኙም ሲገባ቞ው ዹዐፄ ምኒልክ ይቅር ባይነት ዋስትና ሆኗቾው ብዙዎቹ ተመልሰዋል፡፡ ይሁን እንጂ እነኝህ ኚድተው ዚነበሩ ሹማምንት መመለሳ቞ው ዚእውነት ኚልብ ነው ወይስ ለተልዕኮ? ዹሚለው ጉዳይ ለወገን ሠራዊት በወቅቱ እጅግ አንገብጋቢ ጥያቄና እውነቱን ለመሚዳት ኹመቾውም አጋጣሚ በበለጠ አምላክነትን ዚሚያስመኝፀ ሥጋት ጥርጣሬውም እሚፍትና እንቅልፍ ዚሚነሳ አምኖ ለማሰለፍም ለመተውም ያስ቞ገሚበት ጉዳይ ሆኖ ነበር፡፡
  4. ዚፋሜስት ጣሊያን ጩር መሜጎ ያለ መሆኑ፡- ጊርነት በሚደሚግበት ወቅት ጊርነት ኚሚያደርጉት ባላንጣ አካላት አንደኛው ምሜግ ይዞ ዚሚጠብቅ ኹሆነ ጊርነቱ ለአጥቂው ወይም ምሜግ ላልያዘው ክፍል እጅግ ኚባድና አስ቞ጋሪ ዚሚያስኚፍለው ዋጋም ኚመሜገው አካል ጋር ሲነጻጞር በጣም ዹሚበዛ መሆኑ ዹማይቀር ነው፡፡ እኛንም ያጋጠመን ይሄው ነበር በሶስቱም ቊታዎቜ ዚጠላት ጩር ምሜጉን በሚገባ ገንብቶ ኚምሜግ ማዶም በባዶ እግሩ ዹሚጓዘውን አርበኛ ሠራዊት እንዲቆራርጥ በጠርሙስ ስብርባሪና በጩር ቜካሎቜ ኚዚያም በፈንጂ ዚታጠሚ ምሜግ ውስጥ ሆኖ አድፍጊና መሜጎ ይጠብቅ ዹነበሹ ጩር ኹመሆኑ ዚተነሣ ዚጠላትን ጩር ኹዚህ ምሜጉ ለማስወጣት ምን ያህል መሥዋዕትነት ሊጠይቅና ሊያስኚፍል እንደሚቜል መገመት ይቻላል፡፡ እንኳንና ተመጣጣኝ ትጥቅ ሳይያዝ ቢያዝም እንኳ ሁኔታው እጅግ ኚባድ ነው በዚህ ላይ ዚእኛ ጩር ዘመናዊ ዚውጊያ ስልት ካለመማሩ ጋር ተያይዞ ተኝቶ መሬት ላይ በመሳብ መተኮስን እንደ ነውርና ፈሪነት አድርጎ ዚሚቆትር በመሆኑ ደሚቱን ሰጥቶ በኹፍተኛ ድፍሚትና ወኔ ይዋጋ ዹነበሹ ጩር ኹመሆኑ ጋር ተያይዞ መሥዋዕትነቱን እጅግ ዹኹበደ አድርጎት ነበር፡፡ ዹሚገርመው ነገር ግን ኹነዚህ ነባራዊ ሁኔታዎቜ አኳያ ኚጊርነቱ በኋላ ዚደሚሰብን ዚሟቜና ቁስለኛ መጠን በጠላት ሠራዊት ኹደሹሰው እምብዛም ዚሚበልጥ አልነበሚም፡፡
  5. ዹህክምና አገልግሎት ቜግር፡- እንዲህ ዓይነት ዚሕዝብ እንቅስቃሎ በሚደሚግበት ወቅት ወሚርሜኝ ይኚሰታል፡፡ ወሚርሜኝ ሲኚሰትም ለዚህ ጉዳይ ቀድሞ ዹተዘጋጀ ህክምና ኹሌለ ኚባድ ጥፋት አስኚትሎ ያልፋል፡፡ ዹወገን ጩር ይሔንን አደጋ መኹላኹል ዚሚቜልበት አቅምና ዝግጅት አልነበሹም ሌላው ቀርቶ ቁስለኛን እንኳን ማኹም ዚምንቜልበት መድኃኒትና ባለሙያ አልነበሹንም ሁሉም ለዚራሱ ሐኪም ነበሚ፡፡ አስተናግር ቅጠሉን ጹምቆ አዘጋጅቶ ይዞት ዚመጣውን ቁስሉ ላይ እያፈሰሰ እርስ በራሱ ለመተካኚም ይሞክራል እንጅ ይሔንን ጉዳይ ዹሚኹውን ዹህክምና ቡድን አልነበሚም፡፡

እንግዲህ እነዚህና ሌሎቜ ሊታለፉ ዚማይቜሉ እንደተራራ ዹገዛዘፉ ኚባባድ ደንቀራዎቜን ፈተናዎቜን በእግዚአብሔር ቞ርነት በሐበሻነት ጜናት እናት አባቶቻቜን አልፈው ነው ዚአንባላጌውን፣ ዚመቀሌውን፣ በመጚሚሻም ዚአድዋን ድል ለመቀዳጀት ዚቻሉት፡፡ ዚአድዋ ድል በሌሎቜ ዜጎቜ ዘንድም በኹፍተኛ አድናቆት ዹሚደነቀው ዹሚኹበሹውም ኹዚህ ዚተነሣ ነው፡፡

ለመሆኑ ይህ ድል እንዎት ሊገኝ ቻለ?፡- ለድሉ መገኘት ትልቁ ድርሻ ዚእግዚአብሔር ሚድኀት ቢሆንም እግዚአብሔር ሲሠራ በምክንያት ወይም መሣሪያ ዚሚያደርገው ነገር መኖሩ አይቀርምና ለእናት አባቶቻቜን ቁርጠኝነትን፣ ጜናትን፣ መጹኹንን ሰጥቶ ኚቶውንም ዚማይታለፉትን ፈተናና መኚራን አስተናግዶም በእነሱም ደክሞ ደቆ ዹነበሹ ሕዝብ ተሰባብሮ ተነሥቶ እንዲህ ዓይነት አስደናቂ ድል ለማስመዝገብ በቃ፡፡ እንዲህ ዓይነቱን ድል ለማስመዝገብ ሐበሻ ሆኖ መገኘትን ዚግድ ይጠይቅ ነበር አደሚግነውም፡፡ በመሆኑም “ነፃነት ወይም ሞት” “ባሪያ ሆኖ ኹመኖር ነፃ ሆኖ መሞት” ዹሚለው ዹጹኹነ መርሑ ኚፊቱ ዹተደቀኑ ግዛዙፍ ፈተናዎቜን መሰናክሎቜን ኹነ አካ቎ው ኚግምት ውስጥ እንዳያስገባ አድርጎት በኹፍተኛ ቁርጠኝነትና ጜናት በመዋጋቱ ድሉን ሊያገኝ ቻለ፡፡

ዹዚህ ታላቅና አንጞባራቂ ድል ትሩፋቶቜ ምን ምን ናቾው? ይህ ታላቅ ድል ኚእኛም አልፎ ለመላው ዓለም ጭቁኖቜ በርካታ ትሩፋቶቜን አበርክቷል ኚእነዚህ በርካታ ትሩፋቶቹ ጥቂቶቹን ለመጥቀስ ያህል፡-

  1. ዹቀለም ልዩነትን መሠሚት ያደሚገው ዚብቃት ደሹጃ ልዩነት አስተሳሰብን ፉርሜ መሆኑን ማሚጋገጥ ቜሏል፡፡ ኹዚህ ድል አስቀድሞ ጥቁር ሲባል ሰብአዊ እሎት አልባ፣ ለባርነት ዚተፈጠሚ፣ ሥልጣኔ ዚማይገባው አድርገው ያስቡት ነበር፡፡ ኹዚህም አልፈው ተናጋሪ እንስሳ እያሉ ይገልጹት ነበር፡፡ ጥቁሮቹ እናት አባቶቻቜን ግን ፈጜሞ ሊታለፉ ዚማይቻሉ ፈተናዎቜን አልፈው ለክብራ቞ው ለነፃነታ቞ው፣ ለሉዓላዊነታ቞ው ዚማይቜሉት ነገርም እንኳን ቢሆን አንቜለውምና ምን እናድርግ ብለው ክብራ቞ውን፣ ነፃነታ቞ውን፣ ሉዓላዊነታ቞ውን ለድርድር ሳያቀርቡ ለሰብአዊ ክብራ቞ውና ለማንነታ቞ው ታይቶ በማይታወቅ ቀናኢነት በዚትኛውም ዹዓለም ክፍል ያለ ማንኛውም ዓይነት ዹሰው ዘር አደርገዋለሁ ብሎ ሊሞክሹው ቀርቶ ሊያስበው በማይቜለው ሁኔታ በግሩም ቜሎታና ዚአጚራሚስ ብቃት ኹውኖ በማሳዚቱ ጥቁር እንዲህ እንዲህ ነው እዚተባለ ዝቅ ተደርጎ ይቆጠርና ይታይ ዹነበሹው አስተሳሰብ ዚተሳሳተ መሆኑን ዚግዳ቞ውን እንዲያምኑ አድርጓል፡፡
  2. ዚነፃነት ትግልን አነቃቅቷል ቀስቅሷል፡- ጥቁር አፍሪካዊያን ለአምስት ምእተ ዓመታት ያህል በግፈኛ ነጮቜ ሲሰበክላ቞ው ዹኖሹውን ዚጥቁርን ተገዥነት ወይም ለአገልጋይነት መፈጠር አምኖ ተቀብሎ ሰጥ ለበጥ ብሎ ዚመገዛትን አስተሳሰብ አዳብሮ ወደ አውሮፓና አሜሪካ እዚተጋዘ እዚተሞጠ እዚተለወጠ ይገዛ ያገለግል ነበር፡፡ ሐበሟቹ ጥቁሮቜ አድዋ ላይ ያበሩላ቞ው ፀሐይ ግን ይሄንን ዹጹለመ አስተሳሰብ ጠራርጎ በማጥፋቱ ዚነጻነት ትግልንና ዚነፃነት ታጋዮቜን በዚስፍራው በዚአቅጣጫው እንዲቀጣጠል አድርጎ እነሆ ዛሬ ላይ ያን ሁሉ ግፍ በጥቁርነቱ ብቻ ይጋት ዹነበሹው ዹሰው ዘር ነጻነቱን አሹጋግጩ ቢያንስ በገዛ ሀገሩ እንኳን እንደ ሰው መኖር ዚሚቜልበትን ሁኔታ መፍጠር እንዲቜል አብቅቷል፡፡
  3. ዚተሚሳውን ታሪካቜንን አስታውሷል፡- ሐበሻ እንደሕዝብና እንደ ሀገር ኹማንም ዹቀደመ ዚሥልጣኔና ዚመንግሥት ታሪክ ያለውና ዹነበሹው ሕዝብ ነው ይህ ግን በወቅቱ በነበሹው አስገዳጅ ቜግር ሳቢያ ኹዐፄ ፋሲል ጀምሮ ለሹጅም ጊዜ ቆይቶ በነበሹው ዝግ መመሪያ (closed policy) ምክንያት ዓለም እኛን እኛም ዓለምን ሚስተን ተሚሳስተን ስለነበሚ ዓለም በዹጊዜው መሹጃውን እያደሰ እንዳወቀን እዲቀጥል ማድሚግ ሳንቜል ቀርተን ነበር፡፡ ዚአድዋ ድል ግን ዓለም ስለኛ ያለውን መሹጃ ካጎሚበት እያወጣ እንዲያወራ እንዲህ እኮና቞ው እንዲህእኮ ነበሩ እያለ እንዲያወራ አድርጎታል፡፡ ያወሩልን ይፅፉልን ኹነበሹው ታሪኮቻቜን ዹሚበዛው እኛም እንኳን እራሳቜን ዹማናውቃቾው ና቞ው፡፡
  4. ዚሕዝባቜንን አንድነት አጜንቷል፡- ዚጠላት ወሚራ ለመኳንንቶቻቜንና ለመሳፍንቶቻቜን ትልቅ ትምህርትን ሰጥቷል፡፡ በአንድነት ዹመቆምን አስፈላጊነት ዚአንድነትን ጥቅም በሚገባ አስገንዝቧ቞ዋል፡፡ ኚዚያ አስቀድሞ ኹዘመነ መሳፍንት ጀምሮ በመሳፍንቱና በባላባቶቜ ዘንድ ዚዚራሳ቞ውን ጎጥ እንደ ሀገር በመቁጠር ዚዚራሳ቞ውን ‹‹ሀገር›› ዚመመሥሚት ዹማይጠቅምና ኋላ ቀር አስተሳሰብ ያስቡ ነበር፡፡ ይህን ዚትም ዚማያደርስ አስተሳሰብ ለማጥፋት ዐፄ ቎ዎድሮስን እጅግ አድክሟል፡፡ በዐፄ ቎ዎድሮስ እጅ ያደጉት ዐፄ ምኒልክ 2ኛም ዹዐፄ ቎ዎድሮስ 2ኛ ሕልም ገብቷ቞ው ስለነበር ጥሚታ቞ውና ሁኔታዎቜ ፈቅደውላቾው ዹዐፄ ቎ዎድሮስን ሕልም ለማሳካት ቜለዋል፡፡ ዚአድዋ ድልም ለመሳፍንቱ ዚማይሚሳ ትምህርትን ስለጣለላ቞ው ኚዚያ በኋላ አስቀድሞ ዹነበሹው ዓይነት ዚመሳፍንት አስተሳሰብ እንዳይኖር አድርጓል፡፡
  5. ለቀጣይ ትውልድ ታሪክ እንዎት እንደሚሠራና እንደሚጠበቅ ምሳሌነቱን ትቶ አልፏል፡- ሀገራቜን ኹ4500ዓመታት በላይ ዚመንግሥት ታሪክ አላት እንደ ሀገር ኚቆመቜበት ጊዜ ጀምሮ ነጻነቷን ለመንጠቅ ተደጋጋሚና አደገኛ ፈተናዎቜን አሳልፋለቜ፡፡ እነዚሁ ጣሊያኖቜ በቀደመው ስማ቞ው ሮማዊያን ኚቄሳሮቜ ዘመን ኚሁለት ሜህ ዓመታት በፊት ጀምሹው ሲፈታተኑን ኖሚዋል፡፡ ዚአድዋ ድል እናት አባቶቻቜን ዚዚህቜን ሀገር ነጻነት እንደምን ባለ መሥዋዕትነት አስጠብቀው እንደቆዩና ይህ ሹጅም ታሪኳ እንዎት እንደተሠራ ዚቅርብ ጊዜ ምሳሌነት ዹተወ ድል ነው፡፡ በደካማ ጎን መግባት ዚሚቜሉበት ጠላቶቻቜን ግን ዚትግል ስልታ቞ውን በቀጥታ ኚሚተኮሰው አፈሙዝ ወደ ተለዹ ዓይነት በመለወጥና ባንዶቜን በማሠማራት ዚአድዋ ድል ኹተወልን ምሳሌነት ልንማርና እኛም ዚድርሻቜንን ታሪክ ልንሠራ ዚምንቜልበትን ዕድል አጥበውት ሀገርን፣ አንድነትን፣ታሪክን፣ ነጻነትን፣ ሉዓላዊነትን፣ ክብርን መሠሚቱ ያላደሚገ ዹዹግል ዓላማና አስተሳሰብ አራጋቢዎቜ አድርገውን አንድነታቜንን አደጋ ላይ ጥለውታል፡፡በዚህ ሚገድ እዚተሳካላ቞ው ይገኛል፡፡ ፈጣሪ ይቅደምልን እንጂ ዹዚህ ውጀት ደስ ዚሚያሰኝ አይሆንም፡፡
  6. ዚታሪክ ሀብትን ትቶልናል፡- አንዲት ሀገር ዜጎቿ ጠንካሮቜ ኹሆኑ ሁለቱም ሀብቶቜ ይኖሯታል ቁሳዊና መንፈሳዊ ሀብቶቜ ታሪክ መንፈሳዊ ሀብት ነው፡፡ ታሪክ መነቃቃትን ዚሚፈጥር ታላቅ ኃይል ነው፡፡ ቁሳዊ ሀብትም ዹመፍጠር ዐቅም አለው፡፡ ሀገራቜን ኢትዮጵያ ሁለቱም ሀብቶቜ ነበሯት፡፡ ነበሯት ማለቱ ግድ ሆኗል አሁን ላይ ቁሳዊው እንደሌለ ግልጜ ቢሆንም መንፈሳዊው ሀብታቜንም ራሱ ድራሹ እንዲጠፋ በኹፍተኛ ትጋት እዚተሠራበት ነውና ነበሹን ማለቱ ይቀላል፡፡ ሊገባኝ ያልቻለው ነገር ግን ኹዚህ ማን ምን ዓይነት ትርፍ አንዎት ሆኖ እንደሚያገኝፀ ጥቅሙ ምን እንደሆነ ነው፡፡ ለሕዝቡ ልጠይቅ ዚምሻው አንድ ጥያቄ አለኝ  ዚእናት አባቶቻቜን ሀገር ኢትዮጵያ በዓለም  ውስጥ ኚነበሩት አራት  ኃያላን መንግሥታት አንደኛዋ  ነበሚቜ፡፡  ይህቜ ሀገር ዛሬ ዹዓለም  ጭራ ደሀዋ ሀገር ሆናለቜ ለምን? ይህ እንዎት ሲሆን ቻለ? እነሱ ጋር ዹነበሹው ጠንካራ ጎን ይህቜን ደሀና ደካማዋን ኢትዮጵያ ኹፈጠርነው ኚእኛ ጋር ያለው ደካማ ጎን ምንድን ነው?
  7. ዕውቅናና መኹበርን አትርፎልናል፡- ይህ ድል ዚማያውቁን አንዲያውቁንና ሀገር ለሀገር ለሚደሹግ ግንኙነት ተመራጭ እንድንሆን አድርጓል፡፡ ዚሚያውቁንም እንዲያኚብሩን አድርጓል፡፡ ባጠቃላይ ወዳጅ ብቻ ሳይሆን ጠላትም እንዲሁ በተመሳሳይ ሳይወድ በግድ ዕውቅናና ክብር እንዲሰጥ አድርጎታል፡፡ ዚዛሬን አያርገውና ኚዚያ በኋላ ለመጣቜው ኢትዮጵያም ሞገስን አጎናጜፎ በዲንሎማሲው (በአቅንዖተ ግንኙነቱ) ተደማጭ ተኚባሪ እንድንሆን አድርጓል፡፡
  8. ለመሪነት ሚና ተመራጭ እንድንሆን አድርጓል፡- ይህ ድል በሰጠን ዕውቅና ሳቢያ በተለያዚ አቅጣጫ ዚፈጠራ቞ው በቅጭ ግዛት ይማቅቁ ዚነበሩ ሀገራት ዹፀሹ ቅኝ ግዛት እንቅስቃሎ በሚያደርጉበት ወቅት ይህንን እንቅስቃሎያ቞ውንና ትግላ቞ውን እንድንደግፍ እንድናስተባብር ለመጠዹቅ አስገድዷ቞ዋል፡፡ ሀገራቜንም ይህንን ትግል ዚመምራቱን ታሪካዊ ኃላፊነት ሙሉ ለሙሉ በማመን ሀገራቱ ነጻ እስኪወጡ ድሚስ ዚራሷን ዹጩር መሪዎቜንና ተዋጊዎቜን በማሰለፍ ጭምር ትግሉን ስታግዝ ስታስተባብር ዚተጣለባትንም አደራ በሚገባ ተወጥታለቜ፡፡ ለቀድሞው ዹአ.አ.ድ ለአሁኑ አ.ህ እና ለሌሎቜ አህጉራዊና ዓለም ዓቀፋዊ ድርጅቶቜ መቀመጫነት እንድትመሚጥ ያበቃትም ዹዚሁ ድል ትሩፋት ነው፡፡
  9. ሰንደቅ ዓላማቜንን እንድንወስን አብቅቷል፡- በእርግጥ ኚአድዋ ድል አስቀድሞም ዚሀገራቜን ነገሥታት ቀይ ቢጫ አሹንጓዮ ወይም አሹንጓዮ ቢጫ ቀዩን ሰንደቅ ይጠቀሙ እንደነበር ይታወቃል፡፡ ነገር ግን በአዋጅና በይፍ ዕውቅና ተሰጥቶት ሀገራቜንንና ሕዝባቜንን እንድትወክል ዹተደሹገው ዐፄ ሚኒልክ አድዋ ላይ ይህንን አንጞባራቂ ድል ኹገኙ በኋላ እዚያው አድዋ ላይ አዋጅ አስነግሚው ኚእንግዲህ ወዲህ ይህ ቀይ ቢጫ አሹንጓዮ  ሰንደቅ ዚኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማ  ሆኗልና ኚክብር በላይ ክብርን፣ ኹፍቅር በላይ ፍቅርን፣ ኚአለኝታነት በላይ አለኝታነትን ስጧት ብለው በማስነገራ቞ው ይፋዊ ሰንደቃቜን ሆና ለመቀጠል ቻለቜ፡፡

እንግዲህ በአጭር እንቋጚው እንጅ ዚአድዋን ትሩፋት እንዲህ በቀላሉ ዘርዝሮ ዚሚጚሚስ   ጉዳይ አይደለም፡፡ በመቀጠል ዚአድዋ ድል ጠላቶቜ እነማን ናቾው? ዹሚለውንና ይህንን ቅርስ እንዎት ልንጠብቀው እንቜላለን? ዹሚለውን በአጭር በአጭሩ ዐይተን እንቋጭ ፡፡

ዚአድዋ ድል ጠላቶቜ እነማን ናቾው?

ዚእድለቢስነት ጉዳይ ሆኖ ሀገራቜን ኢትዮጵያ ለጠላት ዚታደለቜ ሀገር ነቜ፡፡ በዚህቜ ሀገር በዚትኛውም ሀገር ታይቶ በማይታወቅ መልኩ ለቁጥር ዚሚያታክቱ ጊርነቶቜ ኹውጭና  ኚውስጥ በሚፈጠር ቀውስ ሰበብ አስተናግዳለቜ፡፡ ይህቜ ሀገር ካስተናገደቜው ዚጊርነቶቜ ብዛት አንጻር በታሪኳ በአማካኝ ኹ10 ዓመታት ያለፈ ዹሰላምና ዚእፎይታ ቆይታ ዓይታ አታውቅም፡፡ ተአምር ዚሚሆንብኝ ነገር ቢኖር ይህንን ያህል ዚአውዳሚ ጊርነት ዓይነት ያስተናገደቜ ሀገር ደብዛዋ አለመጥፋቱ ዚሥልጣኔና ዚታሪክ አሻራዎቿም ጥቂቱንም ያህል ቢሆን መቆዚት   መቻላ቞ው ነው፡፡ አሁን ላይ አስቀድሞ ዚነበሩን ጠላቶቻቜንም ሆኑ ሌሎቜ አዳዲስ ቢኖሩ ጥቃታ቞ውን እዚፈጞሙብን ያለው እንደቀድሞው በወሚራ ሳይሆን በመሀኚላቜን ልዩነቶቜ እንዲፈጠሩ በማድሚግና እርስ በእርስ በማናቆር በማፋጀት ሆኗል፡፡ ይሄም ይዞላ቞ዋል፡፡ አርቀውና አስፍተው ማሰብ ዚማይቜሉ ወገኖቻቜን ዚሀገራቜን ዚሕዝብ  ለሕዝብ ግንኙነት  ምንም እንኳን እንኚን ዚለሜ ነበር ማለት ባይቻልም በዚትኛውም ዹዓለም ክፍል ኹነበሹው እጅግ ዚተሻለው እንጅ ተመሳሳይ እንኳን እነዳልነበሚፀ በበቂ ምክንያትና አማራጭም በመታጣቱ ለሀገር አንድነትና ህልውና ሲባል አንዳንድ ዚማያስደስቱን ነገሮቜ መደሹጋቾውን መገንዘብ ማስተዋል ዚተሳና቞ው ደናቁርት ለእነኝህ ጠላቶቻቜን መሣሪያ በመሆን ዚሀገራቜንንና ዚሕዝባቜንን ህልውና ገደል አፋፍ ላይ አድርሰውታል፡፡ ዛሬ ላይ በዚትኛውም ዹዓለም ክፍል ላይ ያሉ ዚባርነትና ጭቆና ቀማሜ ዚነጻነት ደጋፊና አቀንቃኞቜ ዚሚኮሩበትን ዚሚያኚብሩትን ዚሚያደንቁትን  ዚአድዋን ድልና ያንን ድል ያስገኙልንን አርበኞቜ እዚህ ኢትዮጵያ ውስጥ ሆነው በጥላቻ ዚሚመለኚቱ መጥፋት መሚሳቱን ዹሚፈልጉ ለዚህም ዚሚሠሩ ዜጐቜ ለማዚትና ለመስማት ደርሰናል፡፡ መፍትሔው ምንድን ነው ትላላቹ?

ይሄንን ቅርስ እንዎት ልንጠብቀው  እንቜላለን?

ይሄንንና  ሌሎቜ ቅርሶቻቜንን ሀብቶቻቜንን ታሪኮቻቜንን ልንጠብቃ቞ው  ዚምንቜለው ለነዚህ  ሀብቶቻቜን አንድ ዓይነት መግባባት ሲኖሚን ሀብቶቹ በሚገባ ዹመጠበቅ እድል ይኖራ቞ዋል፡፡ አእምሮ ካለን እዚህ አንድ ዓይነት መግባባት ላይ ላንደርስ ዚምንቜልበት እንድም ምክንያት አይኖርም፡፡ ወደራሳቜን ወደ ውስጣቜን እንመልኚት፡፡ እያደሚግነው ያለውን ነገር ኹመፈጾሙ በፊት ዹሚገኘውን ትርፍና ኪሳራ እንመዝን፡፡ እንዲህ እንድናደርግ  እንድንናቆር እንድንባላ ዚሚመክሩን ዹሚገፋፉን ዹሚደግፍን ሀገራት በታሪካ቞ው ኚእኛ ዹኹፋ  ዚእርስ በእርስ ሰብአዊ መብት ገፈፋ ዝጋብ (record)  ያለባ቞ው ሀገራት ና቞ው፡፡ ነገሥታቶቻ቞ው ሲያርፉ ጠባቂ እያሉ ሰዎቜን ኚነነፍሳ቞ው ግራና ቀኝ ይቀብሩ ዚነበሩ ና቞ው፡፡ ዹሰው ልጆቜን ኚአራዊት ጋራ እያታገሉና እያስበሉ ለመዝናኛነት ይጠቀሙ ዚነበሩ ሀገራት ና቞ው፡፡ ይህ ተሞክሮ በሀራቜን ፈጜሞ ኖሮ አያውቅም፡፡ ዛሬ ላይ እነሱ እንኳን አንድ ዓይነት መግባባት ደርሰው በአንድነት   ቆመው ለሀገራቜው ጥቅሞቜ በአንድ ዹተሰለፉ ሆነዋል፡፡ እነሱ ለዚህ ዹበቁ እንደነዚህ ያሉ ዘግናኝና ኢሰብአዊ ድርጊቶቜንና አስተሳሰቊቜን ዓይተን ዹማናውቀው እኛ ኢትዮጵያዊያን እንዎት አንድ ዓይነት መግባባት ላይ ለመድሚስ ያቅተናል? ለሀገርና ለሕዝብ እስካሰብን ጊዜ ድሚስ ፈጜሞ አያቅተንም፡፡ ሀገርንና ሕዝብን ጠልተንና ንቀን ባንዳነትን ኚመሚጥን ግን መቾም ጊዜ ቢሆን ልንግባባና ዹሰላም አዹር ልንተነፍስ አንቜልም፡፡

ዘለዓለማዊ ክብር ለአርበኞቻቜን!!

ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር!!

 

The post ዚአድዋ ድልና ትሩፋት ፈተናዎቹ – ሠዓሊ አምሳሉ ገ/ኪዳን አርጋው appeared first on Zehabesha Amharic.

↧

ወንድሙን ዹሚጠላ ነፍሰ ገዳይ ነው! –ኚኣባ ሚካኀል

$
0
0

ዚካቲት ፳፫ ቀን ፪ሺህ፯ ዓም

ተፃፈ ኚኣባ ሚካኀል።

love቞ሩ መድኃኔ ዓለም ይመስገንና እርሱ በመጀመሪያ ዹሰውን ዘር ኹዘለዓለማዊ ሞት ሊታደግ ሲመጣ ዓለሙ በሙሉ እርሱን ደስ ዚማያሰኝ ዚጌታ ጠላት ነበር። ጌታ መድኃኔ ዓለም ግን ለሰው ልጅ ያለው ፍቅር እርሱን ኹዙፋኑ ስለሳበው ዕውነተኛ ዹፍቅር መሥዋትን ይህቺውም ሕይወቱን ኣሳልፎ እስኪሰጥ ድሚስ ወድዶናል፥ በደሙም ነፃ ኣውጥቶናል።  ሕግ ሁሉ በፍቅር ስለሚፈጞም ጌታ እርስ በርሳቜሁ ተዋደዱ ካለን በኋላ ጌታቜን ያለውፊ እኔንስ ብትወዱ ትዕዛዜን ጠብቁ ነው፥ በዕውን ትዕዛዙን ጠብቃቜኋል?

ዛሬ በኢትዮጵያ ሃገራቜሁ ውስጥ ፖለቲካው ባመጣባቜሁ በደል ምክንያት በተኚበራቜሁበት ሃገራቜሁ ላይ ለመኖር ስላልቻላቜሁ በዐራቱም ማዕዘናት ተሰድዳቜሁ ባላቜሁበት ክፍለ ዓለማቶቜ ሁሉ ኃይማኖታቜሁን ጠብቃቜሁ ቀተ ክርስቲያኖቜንና መስጊዶቜን ኚፍታቜሁ እዚተገለገላቜሁ ትገኛላቜሁ። ይህንንም በማድሚጋቜሁ እራሳቜሁን ታድጋቜኋልፀ ይህም ለጊዜው መልካም ነው፥ ምንም ቢሆን እንደ ዕራስ ሃገር ኣይሆንምና።

ባላቜሁበት ሥፍራ ሁናቜሁ ደግሞ ዚሃገራቜሁን ውሎና ኣዳር በትጋት ትኚታተላላቜሁ። ሁላቜሁም “በዚያቜ ሃገር” ላይ ሳይሆን በኢትዮጵያ ሃገራቜሁ ላይ ሠላም ወርዶና እርቅ ተደርጎ መቻቻልን ዹተዋሃደ ሕዝባዊና ፍህታዊ ዹሆነ መንግሥት ፈጥራቜሁ እንዲሁም ዚመኚላኚያ ኃይሏ ለሕዝቧ እንዲያገለግል እንጂ ሥልጣን ላይ ዚሚወጣውን ጥቅም ኣስኚባሪ እንዳይሆን ቀርጻቜሁ ወደ ሃገራቜሁ ተመልሳቜሁ ተኚብራቜሁና ኣክብራቜሁ መኖርን ትሻላቜሁ።

በውድ ሃገራቜን ላይ እንጂ በባዕድ ሃገር ላይ ኣንኖርም ያሉና በኢትዮጵያ ውስጥ ዚሚኖሩትን ዚእህቶቻቜሁንና ዚወንድሞቻቜሁን ሕይወት ስናይ ደግሞ ነፃነታቜውን ለማግኘትና እናንተም በዚሃገሩ ተበትናቜሁ ዚምትገኙትን ወደ ሃገራቜሁ እንድትመለሱ በሚያደርጉት ትግል ላይ እናንተ ዚፈራቜሁትንና ኹሃገር ያሳደዳቜሁን ህዋሓትፊ እነርሱ በጠራራ ፀሐይ እዚተጋፈጡት ድብደባ፣ እስራት፣ መሞማቀቅ፣ ሚሃብ ወዘተ ብቻ ሳይሆን ኹፍተኛውን ዹፍቅርን ዋጋ ሞትን እዚሞቱላቜሁ ይገኛሉ።

ዹሚገርመኝ ቢኖር ክርስቲያኖቜ ወይም ሙስሊም ሆናቜሁ ሳለ ጠላትህ ቢራብ ኣብላው፣ ቢጠማም ኣጠጣው፣ ቢራዝ ኣልብስው /ሮሜ ፲፪ ቁ ፳/ ዹሚለው ዚኣምላክ ቃል በዹጊዜው እዚተሰበኚላቜሁ ጠላቶቻቜሁ ሳይሆኑ ዹገዛ ወንድሞቻቜሁ እንኳን ቢራቡም፣ ቢጠሙም፣ ቢራቆቱም፣ በግፍ ቢገደሉም ወዘተ ፓትርያርኩም፣ ጳጳሱም፣ ቄሱም፣ ፓስተሩም፣ ሌሁም፣ ኢማሙም እንዲሁም ምዕመኑ ዝም። እግዚዖታን እንኳን ነፈጋቜሗቜው።  በሃገር ቀቱስ ላሉት ውስጡን ለቄስ ነው፥ ህዋሓት ናት ዚሓይማኖቱን ሥራ ዚምትሠራው። ኚሃገራቜሁ ዕርቃቜሁ በነፃነት ዚምትኖሩ ክርስቲያኖቜ እስቲ ቆም በሉ። በእውን ዚሞተላቜሁን ክርስቶስን ትወዱታላቜሁ? ትዕዛዙንስ ትፈጜማላቜሁ? ኣምላካቜሁ ክርስቶስ ለሞተላት ክብርት ቀተ ክርስቲያን ፍቅር ኣላቜሁ? ወይስ ኚኢትዮጵያ ጠላት ጋር ኣብሮ ዹወገኑ ሞት ለእርሱ ሕይወት እንደ ሆነለት ሆድኣደር ሆናቜሁ? ሙስሊሞቜስ?

ህዋሓት ዛሬ ሳይሆን ኚ፳፬ ዓመት በፊት ጀምራ ዚኊርቶዶክስ ክርስቲያንና ዚእስልምናን ዕምነት ለማጥፋት በሚገባ ዚቀት ሥራዋን ሠርታ ዛሬ በተግባር እዚተሚጎመቜው ነው። ንዋዹ ቅዱሳኖቜን ኣውጥታ ሜጣለቜ፣ ቀተ ክርስቲያንን ኣቃጥላለቜ፣ መነኮሳትን ኚገዳም ድሚስ በመሄድ ደብድባለቜ፣ በቅርቡም ኢትዮጵያ ካለው ሲኖዶስ ይልቅ ለኊርቶዶክስ ቀተ ክርስቲያን በሃገር ቀት ግልጋሎት ዹሚሰጠውን ማኅበሹ ቅዱስንን ልትመታ ቃጥቷታል፥ ምንም እንኳን ማኅበሹ ቅዱሳን ኹሃገር ቀት ውጪ ዚተኚፈቱትን ኣብያተ ክርስቲያናት ህዋሓት በሚቆጣጠሚው በሃገር ቀቱ ሲናዶስ ሥር እንዲተዳድሩ በማድሚግ ኹፍ ያለ ሚና ቢጫወትም ለህዋሓት ማኅበሹ ቅዱሳን ኚኣብዮታዊ ዲሞክራሲው ኣይበልጥበትምና ኚ፪ሺህ፯ ምርጫ በውኋላ ተመልሳ ዚቃጣቜውን በተግባር ልታውል ትቜላለቜ ብዬ እገምታለሁፀ እስልምና ኃይማኖትን ዚሚመሩትን ትመርጣለቜፀ ፕሮ቎ስታንቶቹን ደግሞ ኣንድ ቀን መንካቷ ኣይቀርም።

እስቲ እዩ፥ በኣካባቢያቜሁ ስለ ኢትዮጵያ ዚሚያስቡትንና ኢትዮጵያን ነፃ በማድሚግ ኃይማኖት እና ፖለቲካ ተኚባብሚው በኢትዮጵያ ውስጥ እንዲኖሩ ደማቾውን ኚሚያፈሱት ጋር ኣጋር በመሆን ጊዜያ቞ውንና ገንዘባቜውን ለትግሉ መሳካት ዚሚሰጡትን፣ ስለ ወገናቾው ግድ ዚሚላ቞ው፣ ስለ ኃይማኖታቜውም ስለ ሃገራ቞ው ፖለቲካም ቢናገሩ ዕውነተኞቜና ታሪክ ሠሪዎቜን፣ ህዋሓት እስካለቜ ሃገሬን ባላይስ መጀመሪያ ነፃነቮን ያሉትን። በኣንፃሩ ደግሞ እናንተ ዛሬ ገንዘብ ኣግኝታቜሁ ቀት በሃገር ቀት ስትሠሩና ንብሚት ስትመሠርቱ ወደ ሃገር ቀት ዚምትልኩት ዚውጪ ምንዛሪ ዚህዋሓትን ዹጭቆና ሥርዓት እንደሚሚዳ እያወቃቜሁ ስለራሳቜሁ ብቻ ትጚነቃላቜሁ። ገንዘባቜሁ ባለበት ምናቜሁ ኣብሮ ይኖራል ኣለ? ህዋሓት እንዲህ እያሚገቜ ነው ዚምትቆጣጠራቜሁ።

ኚሃገራቜን ተኚትሏቜሁ ዚመጣው ዚፖለቲካ ቜግር ደግሞ ዚኊርቶዶክስ ቀተ ክርስቲያናቜሁን በሊስት ቊታ ኚፍሏታል። ኣሁን ባላቜሁበት ሃገር ዚኣቡነ ማቲያስ ሥም ዚሚጠራባ቞ውን ቀተ ክርስቲያኖቜን ብትመለክቱ፥ ወይ በበላይነት ወይም በኃላፊነት ላይ ያሉት ካህናቶቜና ግለሰቊቜ ዚህዋሓት ደጋፊዎቜ ናቜው። በመሆና቞ውም፥ ምዕመኑን በተቻላ቞ው መጠን ኢትዮጵያን ኚህዋሓት እንዳያላቅቅና ወደ ተቃዋሚ ዚትግሉ ጎራ እንዳይሄድ ኣድርገውታል። ኣይ ሃገራቜን መልካም ኣስተዳደር ኣላት ትግሉ ኣያስፈልግም ዚምትሉ ካላቜሁ ግን ለምን በሃገራቜሁ እንደማትኖሩ ይገርመኛል፥ ሌላ ተልዕኮ ኚሌላቜሁ በስተቀር።

በምን ሰሌት እያሰላቜሁ ነው ህዋሓት ኚምትመራው ሲኖዶስ ጋር ተሰልፋቜሁ ቀተ ኚርሰቲያኒቷን  እያጠፋቜኋት ያላቜሁት። ባለፈው ሣምንት ውስጥ ኚእንጊጊ ኪዳነ ምህሚት ቀተ ክርስቲያን ውስጥ ዕድሜ ጠገብ ወርቆቜ ወዘተ ለኣባይ ግድብ መዋጮ ተወሰዱ ዹሚል ዜና ሰማሁ ግን ኣቡነ ማቲያስ  ኚጜህፈት ቀታ቞ው ስለዚህ ጉዳይ ያወጡት መግለጫ ዚለም። እናንተ ዚእርሳ቞ውን ሥም በማንሳት ዚምትተባበሩትስ ምን ኣላቜሁ? ምንም። ቀተ ክርስቲያኗስ ኣትጠፋም፥ ኣንዎ በክርስቶስ ደም ላይ ተመሥርታለቜና፥ ውዮ ግን ለእናንተ ዚኣምልኮ መልክን ብቻ ለያዛቜሁ፥ ለወገናቜሁ ስቃይ ሳይሆን ስለራሳቜሁ ብቻ ለምትጚነቁ።

በውጭ ሃገር ሲኖዶስ መቋቋሙን  ባንደግፈውም ዚኣቡነ መርቆርዮስን ፓትርያርክነት ዚሚክዱት ህዋሓት ዚሰለበቻቜው ዚዋሆቜ ካልሆኑ በስተቀር ኣሁንም ቢሆን ሕጋዊው ፓትርያርክ እንደሆኑ ሌሎቻቜን እንሚዳዋለን። ይህንንም ዚውጪውን “ሲኖዶስ” ደግሞ ጠጋ ብሎ ላዹው ሰው፥ ዹጎንደር ሃገር ስብክት እንጂ ዚኢትዮጵያ ሲኖዶስ ለመባል ዚሚቜል ስብስብ ኣይደለምፀ እንዲሁም ለወደፊቱ ፓትርያርክ ለመተካት እንኳን ሥልጣን ዚለውም።  እዛ ጊዜ ላይ ቢደሚስ፥ ዹገለልተኛው ቁጥር ኚሌሎቹ እንደሚበልጥ እገምታልሁ።

ለዚህ ሁሉ ቜግር መንስኀ ዚሆነቜውን ህዋሓትን በማስወገድ ነፃነታቜሁን ማወጅ ኣማራጭ ዹሌለው መንገድ ነው። ኣቋማቜሁን ኣስተካክላቜሁ ስለ ኢትዮጵያ ጉዳይ ስብሰባ ስትጠሩ በስበሰባው ላይ ተገኙና ስለ ኃይማኖታቜሁና ስለ ሃገራቜሁ ያገባናል በሉ። በፀሎትና በሃሳብ እንዲሁም በገንዘባቜሁ ወገኖቻቜሁን ታደጉ። ካህናቶቻቜሁ በሃገር ቀት ዹሚደሹገውን ግፍ ኃይማኖትን በጠበቀ መልኩ እንዲያወግዙ ግዎታ ኣለባ቞ውና ይህንን እንዲያደርጉ ጫና መፍጠር ኣለባቜሁ። ካህናቶቹ ይህንን ባያደርጉ ግን፥ ስለ ኢትዮጵያ ህዝብ ግድ ኹሚላቾው ካህናቶቜ ኚሚያገለግሉበት በመሄድ ዚሕብሚት ጞሎት በማድሚግና በተግባር ደግሞ ሰለ ኢትዮጵያ ነፃነት ኚሚታገሉት ጎን በመቆም ዕውነተኛ ፍቅርን በማሳይት ትዕዛዝ ማክብራቜሁን ኣሚጋግጡ።

ተፃፈ ኚኣባ ሚካኀል።

 

 

The post ወንድሙን ዹሚጠላ ነፍሰ ገዳይ ነው! – ኚኣባ ሚካኀል appeared first on Zehabesha Amharic.

↧

ሙስሊሞቜና ክርስቲያኖቜ ዚተሳተፉበት ዚስልክ ጥሪ ማቆም አድማ ተካሄደ

$
0
0

10920943_352316331618819_5078649879608517565_nዚካቲት ፳(ሃያ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ሰሞኑን እንዳዲስ ተጠናክሮ በቀጠለው ሙስሊም ኢትዮጵያውያንን ዹማሰር ዘመቻውን በመቃወም ድምጻቜን ይሰማ ዚጠራው ስልክን ለ12 ሰአታት ዚማጥፋት ዘመቻ በተሳካ ሁኔታ መካሄዱን ዘጋቢያቜን ገልጿል፡፡

በርካታ ሙስሊሞቜ ስልኮቻ቞ውን አጥፍተው ዹዋሉ ሲሆን፣ በማህበራዊ ዹመገናኛ ብዙሃን ዚሚያደርጉትን እንቅስቃሎም አቁመው ውለዋል። በርካታ ክርስቲያኖቜም ጥሪውን ደግፈው ስልካ቞ውን ዘግተው ውለዋል።

እርምጃ ዚመንግስት ዋነኛ ዚገቢ ምንጭ በሆነው ቮሌ ላይ ዚኢኮኖሚ ጉዳት ለማድሚስ ታቅዶ ዹተተገበሹ ነው።

Source:: Ethsat

The post ሙስሊሞቜና ክርስቲያኖቜ ዚተሳተፉበት ዚስልክ ጥሪ ማቆም አድማ ተካሄደ appeared first on Zehabesha Amharic.

↧

በአማራ ክልል ነዋሪዎቜ በአገልግሎት ሰጪ ድርጅቶቜ መማሚራ቞ውን ተናገሩ

$
0
0

Amharamapዚካቲት ፳(ሃያ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በክልሉ ኢንዱስትሪና ኹተማ ልማት ቢሮ እና ዚተለያዩ ቢሮዎቜ በዚእለቱ ጉዳያ቞ውን ለማስፈጞም ዚሚመላለሱ ባለጉዳዮቜ በተለያዚ ሰበብ ፈጻሚ በማጣት መ቞ገራ቞ውን ድርጅቱ ባዘጋጀው ዚአስተያዚት መስጫ መዝገብ ላይ ማስፈራ቞ውን ኚስፍራው ዹደሹሰን መሹጃ ያሳያል።

ኚተለያዩ አካባቢዎቜ ጉዳይ ለማስፈጞም እንደመጡ ዚገለጹት ቅሬታ አቅራቢዎቜ በተለይ በስብሰባ ሰበብ ለሚዢም ጊዜ መጉላላታ቞ውን ባሰፈሩት ዚሃሳብ መስጫ ደብተር ላይ ለማንበብ ይቻላል። አስተያዚት ሰጪዎቜ በዋነኝነት ያነሱት ቜግር ባለስልጣኖቜ በስብሰባ ሰበብ ባለጉዳይ ለማስተናገድ አለመቻላ቞ውን ሲሆን፣ ዚብቃት ማነስም ቜግርም ተጠቅሷል።

“ለማን ብሶታቜንን እንናገር ፣ ጠዋት ስንመጣ ኚሰአት ኚሰዓት ስንመጣ ጠዋት፣ ቢሮ ኃላፊው ዚለም፣ ሂደት አስተባባሪው ዚለም፣ ዚድርጅቱና ዚመንግስት ሚዲያ በዚመድሚኮቜ ሚናገሩት ሌላ ፣


ዹኹተማው ህዝብ በመሬት እጊት፣ ዚመንግስት ሰራተኛው በደመዎዝ ማነስና ፣ተመርቆ ኚቀተሰቡ ጋር ቁጭ ብሎ በመቅሚቱ ዚገጠሩ ህብሚተሰብ በማዳበሪያ ውድነት ተወጥሮ ፣ በሌትና በቀን ዹቁም ቅዠት አያሰቃዚው አሁን ለማን ነግሮ መፍትሄ ያገኛል? ለመንግስት ቢነግሩ ኚወሚቀት ዹዘለለ ዚተግባር ፍሬ ዹለውም ኧሹ ለማን እንንገሚው?አምላክ አይፈጥን እንደሰው!እባክህ ጌታዬ ዚኢትዮጵያ አምላክ በ2007 ምርጫ ገላግለን ፣ በ቞ርነትህ መንግስት በዘር በዘመድ አዝማድ በገንዘብ እዚተሞበበ በቁማቜን እዚተጓዝን ተቀበርን፡፡


..ለአመራሮቜ በጣም ኹፍተኛ ዹሆነ ስልጠና ሊሰጣ቞ው ይገባል፡፡ ባለስልጣኖቹ ድሃውን ህዝብ በማንገላታት ዚታወቁ መሆናቾው በአለም ታውቋል ዚነሱን ም቟ት ካገኙ ለሌላው ምንም ደንታ ዹላቾውም




..ባሁኑ ሰዓት አቀት ባይ ሲበዛ ፍትህ ሰጪ ግን ዚለም፡፡ለምን ይሆን ህብሚተሰቡን ዚተጣላው?እግዛብሄር ይሆን መንግስት ነው አልገባኝም  .

ዚሚሉት አስተያቶቜን ዚያዙ ማስታሻዎቜ ለስሙ በተቀመጡ ያአስተያዚት መቀበያ ደብተሮቜ ላይ ሰፍሹው ይነበባሉ፡፡

ዚገዢው መንግስት ባለስልጣናት ኚህዝቡ አስተያዚት በመሰብሰብ አገልግሎት አሰጣጣቜንን እናስተካክላለን እያሉ ቢናገሩም ዚአስተያዚት ደብተሮቜን እንደማይመለኚቱ አስተያዚት ሰጪዎቜ ገልጞዋል፡፡

Source:: Ethsat

The post በአማራ ክልል ነዋሪዎቜ በአገልግሎት ሰጪ ድርጅቶቜ መማሚራ቞ውን ተናገሩ appeared first on Zehabesha Amharic.

↧
↧

ኹፍተኛ ቁጥር ያላ቞ው ዚሰቆጣ አርሶደአሮቜ በሚሃብ ምክንያት ተሰደዱ

$
0
0

esat

esat 2

ESAT 3
ዚኢሳት ወኪል እንደዘገበው በሰቆጣ አካባቢ ዹተኹሰተውን ኹፍተኛ ድርቅ ተኚትሎ አርሶደአሮቹ ወደ ምእራብ ጎጃምና ሌሎቜ ዚአማራ ክልል አካባቢዎቜ በመሰደድ ላይ ና቞ው።

ተፈናቃዮቹ ኹክልሉ ባለስልጣናትም ይሁን ኚፌደራል መንግስቱ ምንም አይነት እርዳታ አለማግኘታ቞ውን ገልጞዋል።

ብዙዎቹ ተፋናቃዮቜ ወጣት ወንዶቜና ሎቶቜ ሲሆኑ፣ በሰፈሩባ቞ው አካባቢዎቜ ስራ ሰርተው ራሳ቞ውን እንዲያስተዳድሩ እዚጠዚቁ ነው።

ተፈናቃዮቹ በዝናብ እጥሚት ምክንያት ሰብላ቞ው ሙሉ በሙሉ መውደሙን ገልጞዋል።
መንግስት በአካባቢው ስለተኚሰተው ድርቅ እስካሁን ዹሰጠው ምንም አይነት መልስ ዚለም።

The post ኹፍተኛ ቁጥር ያላ቞ው ዚሰቆጣ አርሶደአሮቜ በሚሃብ ምክንያት ተሰደዱ appeared first on Zehabesha Amharic.

↧

ዚጉራጌ ካድሬዎቜ አንገታ቞ውን ያስደፋ ክስተት

$
0
0

‹‹ያለ ኢኮኖሚ ዚበላይነት ዚፖለቲካ ዚበላይነት አይመጣም››

ዹሚለው ዚህውሃት ኢህአዲግ ፖለቲካ ኢኮኖሚውን ኚመቆጣጠር ባለፈ ደጋፊዎቹን በኢኮኖሚ በማብቃትና በተጠቃሚነታ቞ውም ፖለቲካውን በመጠበቅ ዚበሚኛነት ሚና እንዲጫወቱ በ97 ምርጫ ማግስት ኚተወሰዱትርካሜ እርምጃዎቜ አንዱ በግምታዊ አቀማመጥ መሃኹለኛ ገቢ ያላ቞ውን ዚመርካቶ ጉራጌዎቜ በማዳኚም ዚህውሃትን ተጠቃሚዎቜ ማጠናኹር ነበር::
Ethiopia
ዚወቅቱ ዚኮሚኒኬሜን ሚኒስትር ዲኀታ ኀርሚያስ ለገሰ ይህንን ይላል በምርጫ 97 ማግስት አቶ መለስና በሚኚትን ጚምሮ ኹፍተኛ ዚኢህአዎግ ካድሬዎቜ ‹‹ጉራጌ አብዮት አካሄደብን›› በማለት ይናገሩ ነበር፡፡ በኢህአዎግ ማእኚል በተዘጋጀው ሰነድ ላይ ዚጉራጌ ብሄሚሰብ ኚትምክህት ጎራ ጋር በተቀላቀሉ ልጆቹ ምክንያት ዹሀይል አሰላለፍ ቀውስ ውስጥ በመግባት ኚጥገኛ ኃሎቜ ጋር ተሰልፎ ወደ ዝቅጠት ገብቶ እንደነበር ይገልጻል፡፡ በመላ ሀገሪቱ ዹሚገኙ ዚብሄሚሰቡ ተወላጆቜ(በጉራጌ ዞን ያለውን መዋቅራቜንን ጚምሮ) ዚዜጎቜን በነጻነት ዚማሰብና ዚመምሚጥ መብት በመጋፋት እስኚ ጎጣ቞ው በመሄድ ‹‹ኢህአዎግን ዹመሹጠ ውሻ ይውለድ!›› ዹሚሉ ቃል ኪዳኖቜን እስኚ ማጥለቅና መማማል ዘልቀው ነበር በማለት ይኚሳ቞ዋል፡፡ ዚጉራጌ ብሄሚሰብ እንደ ሌሎቜ ዚሀገራቜ ጭቁን ብሄሚሰቊቜ ህገ-መንግስታዊ መብቱ በተኚበሚበት፣ ራሱን በራሱ ዚማስተዳደር መብት በተጎናጞፈበት ሁኔታ ወደ ትምክህት ሀይል ሜግሜግ ማድሚጉ ያልተጠበቀ እንደነበር ሰነዱ አመላኚተ፡፡( ቅንፍ ዚራሎ በምርጫ ኢህአዎግን አለመምሚጥ መብት ሳይሆን ትምክህተኝነት ዚሚባል ሃጥያት ነበር ዛሬም ነው)

በቀሹበው ዶክመንት ላይ በመመስሚት በዚወሚዳው ዚተካሄዱት መድሚኮቜ አስደንጋጮቜ ነበሩ፡፡ ዚምርጫ 97 ውጀት ዚኢትዮጵያ ህዝቊቜ ዚትግ ውጀት መሆኑን በመካድ ‹‹ጉራጌ መራሜ አብዮት›› ዹሚል ስያሜ እስኚ መስጠት ተደሚሰ፡፡ ጣቶቜ በሙ ወደ ጉራጌ ብሄሚሰብ በተለይም ዚብሄሩ ተወላጅ ዚኢህአዎግ ካድሬዎቜ ላይ ተቀሰሩ፡፡ ነጋዮው ጾሹ-ኢህአዎግ እንዲሆን ኚአመታት በፊት ዹተጠነሰሰ ሎራ እደሆነ በሰፊው ተነገሚ፡፡ ዚጉራጌ ካድሬዎቜ አንገታ቞ውን ደፉ፡፡

ኢኮኖሚውን ዚሚቆጣጠር ኃይል በሂደት ፖለቲካ ኢኮኖሚው ላይ ዚበላይነት ማሳሚፉ ስለማይቀር ጉራጌን ኚንግዱ ዓለም ማስወጣት ለጥያቄ ዚሚቀርብ አይደለም፡፡ ሮማን (ዚህወሃት ባለሃብቶቜን መፍጠር አላማ አስቀጣይ ዚሆነቜ) ዚጉራጌ ነጋዎዎቜን እንዳያሰራሩ ዚምትቀጣበት ምክንያት ይህ ነበር፡፡
እነ ሮማ በፈጠሩት ልዩነት ጉራማሌዋ መርካቶ ይበልጥ ተዘበራሚቀቜ፡፡ ተመሳሳይ እቃዎቜ በነባሮቹና አዲሶቹ ነጋዎዎቜ መካኚል ዹዋጋ ልዩነት አሳዚ፡፡ ዚግብርና ዹሊዝ እፎይታ ያገኙት አዲሶቹ ነጋዎዎቜ ዋጋቾውን አወሚዱ ሞማቹሚስጥሩ ሳይገባው ቅናሜ ወዳገኘበት አዲሶቹ ነጋዎዎቜ ፊቱን አዞሚ፡፡ ቀስ በቀስ ነጋዮው ኚገበያ ወጣ፡፡
ዚማፊያ ባህሪ ያላ቞ው አዲሶቹ ነጋዎዎቜ ሰው ሰራሜ እጥሚት በመስኚሰትም ተወዳዳሪ አልነበራ቞ውም፡፡ በሰአታት ውስጥ አንድ ኪሎ ጹው ዋጋ ኚአንድ ብር 50 ብር ዚተሞጠበት አጋጣሚ ልብ ይሏል፡፡

ነባሩ ነጋዮ ኚገበያ መውጣቱ እልህ ዚተጋቡት ዚጉራጌ ካድሬዎቹ እነ ሺሰማ ክትትል ማድሚግ ይጀምራሉ፡፡ ኚብዙ ጥሚት በኋላ ሞፍጥ ዚሚሰራበትን ቊታ ይደርሱበታል፡፡ ሮማንና ወዳጆቿ ፋይል ዹሚሰርዙና ዚሚደልዙት፣ ግብር ዚሚጚምሩትና ዚሚቀንሱት፣ ሱቅ ዚሚሰጡትና ዚሚቀሙት አምባሳደር ፊልም ቀት ዹሚገኘው ካፍ቎ሪያ ዚሕገወጥነቱ ማዕኹል ነበር፡፡ .

ኚምርጫ 97 በኋላ ዚጉራጌ አብዮትን ለመቀልበስ በስብሰባ ማዕኹል በተጠራ ዚመጀመሪያው ዙር ማጠቃለያ ኮንፍሚንስ ላይ ተገኝቌ ነበር፡፡ በጉባኀው ዚተሳተፉት ኚአንድ ሺህ በላይ ዚጉራጌ ነጋዎዎቜና ባለሃብቶቜ ነበሩ፡፡ ይህን ለአንድ ሳምንት ዹዘለቀ ጉባዔ ዚመራው ዶ/ር ካሱ ኢላላና ሚኒስትር መኩሪ ነበሩ፡፡ ነጋዎዎቜ በሲቃ ስለ ሮማንና ሉሌ ዚሚነሱት ወንጀል ጚጓራ ዚሚልጥ ነበር፡፡ በተለይ ዹክፍለ ኹተማው ዚገቢዎቜ ኀጀንሲ ሙያተኛ ዹሆነ ዚጉራጌ ተወላጅ ስራዚን ለመልቀቅ ብዙ ተሟግቻለሁ በማለት ዹገለጾው ታሪክ ዶ/ር ካሱ አንገቱን አቀርቅሮ አንዲቀር አድርጎታል፡፡ ኚመቀመጫው ተነስቶ ዚኮንፈሚንሱን ተሳታፊ አንባ እዚተናነቀው ይቅርታ ጠይቋል፡፡

እንዲህ ነበር ያደሚጉት፣
ሎሌና ሮማን ኚቢሮአ቞ው ሳይወጡ ኚአስር እጥፍ በላይ ግብር እንዲጥሉ ሙያተኞቜን አስገደዱ፡፡ ኚስሚው ለመዘጋት አፋፍ ላይ ያሉ ነጋዎዎቜን ኚግብር ሕጉ በተቃራኒ ታክስ አስኚፈሉ፡፡ በድርጊቱ ዚተበሳጚ አንድ ነጋዮ ራሱን በገመድ አንጠለጠለ፡፡ ተመሳሳይ ሱቅና ዚንግድ ዓይነት ያላ቞ውን ጎሚቀት ነጋዎዎቜ አንዱን በዜሮ ፣ሌላውን በአስር ሺዎቜ ታክስ እንዲኚፍል አድርገዋል፡፡ ይህ በዘር ላይ ዹተመሰሹተ እርምጃ ቀድሞ በነጋዎዎቜ ዘንድ ዹነበሹን በደጋገፍ እንዲቀር በማድሚግ እርስ በራስ በጥላቻ እንዲተያዩ አድርጓል፡፡ በዚህ ምክንያት መሳሪያ ዚተማዘዙ፣ በገጀራ ተፈነካክተው ወህኒ ዚወሚዱ ነጋዎዎቜ ይገኙበታል፡፡

(ለግምገማ ቀርባ ዚነበሚቜው ሮማን እንዳትጠዚቅ አርኹበ ተኹላክሎ አትርፏታል)

The post ዚጉራጌ ካድሬዎቜ አንገታ቞ውን ያስደፋ ክስተት appeared first on Zehabesha Amharic.

↧

ኹሃሹር እስኚ ጎዮ እንዲሁም ሃርጌሳ አፈሳው እና አፈናው ተጥውጡፏል

$
0
0

(ምንሊክ ሳልሳዊ) ባለፉት ቀናቶቜ ውስጥ ወያኔ እና ዹኩጋዮን አማጺ ሃይሎቜ ያደሚጉትን ጊርነት ተኚትሎ ኚግድያው በተጚማሪ ኹሃሹር እስኚ ጎዮ ያካልለ ዚመንገድ ላይ አፈሳ እና ዚቀት ለቀት አፈና እዚተካሄደ እንደሆነ ኚሰራዊቱ እስጥ ዚሚገኙት ወታደራዊ ደህንነቶቜ ተናግሹዋል::
news
በልዩ ሃይል መሪነት እና በሕወሓት ጩር ተባባሪነት እዚተፈጞመ ያለው አፈሳ እና አፈና ዚወያኔ ጩር ባልውፉት ቀናት ዚደሚሰበትን ሜንፈት እና ኪሳራ ለማካካስ ዹጀመሹው ሲሆን እስካሁን ዚቀት እመቀቶቜን ጚምሮ ኹ400 ሰዎቜ በላይ ተይዘው መታሰራ቞ው ሲነገር ዋና ዋና ናቾው ዚተባሉ ዹኩጋዮን አማጺ ሃይሎቜ አባላት ወደ መሃል አገር መላካ቞ው ታውቋል::በዚህም መሰሚት ዚስለላ ስራ ያካሂዳሉ ዚተባሉት አጋስ መሃመድ አብደላ እና አብዱላዚዝ አብዶ ቀሜር ዚተባሉ ዚአማጺ አባላት ይገኙበታል::አፈሳው እና አፈናው በሃሹር በጎዮ በቀብሪበያህ በቀብሪ ደሃር በጅጅጋ በሃርሾክ እና በሰሜን ሱማሊያ ሃርጌሳ እዚተካሄደ እንደሆነ ምንጮቹ ገልጾዋል::

በአንድ በኩል እንደራደር እያለ በአንድ በኩል በውጊያ ዹሚጠዛጠዘው ሰው በላው ወያኔ ምን ያህል ዚፖለቲካ ኪሳራ እና መበስበስ እንደሚጠቁም እና ዹኩጋዮንን ነዋሪዎቜ እያፈነ እና እያሰቃዚ በዚትኛው ዹሞላር ሚዛን ድርድር ላይ እንደሚቀመጥ እና ኚነማንስ ነው ዚሚደራደሚው ዹሚለው ጉዳይ ጥያቄ አስነስቷል::

ካለፈው ሳምንት ጀምሮ በኩጋዮን አማጺ ሃይሎቜ እና በወዹኔ ጩር መካኚል በኩጋዮን ደገሃቡር አኚባቢ ኹፍተኛ ውጊያ መካሄዱ ሲታወቅ በሰጋጋ አኚባቢ ዹኩጋዮን አማጺ ሃይሎቜ ኮማንደር ተገለዋል:: ዚአማጺ ሃይሎቜ ተዋጊዎቜ በአኚባቢው ኹሚገኘው ልዩ ሃይል ተብሎ ኚሚጠራው እና በወያኔ ጩር ጋር ዚአኚባቢው ነዋሪዎቜ መታፈና቞ውን ተኚትሎ ኹሃሹር ኹተማ 160 ኪሎሜትር ደቡብ ምስራቅ በምትገኝ በአኪርሚሜ ላስጋሎል በተባለ ቊታ መዋጋታ቞ውም ይታወሳል::

The post ኹሃሹር እስኚ ጎዮ እንዲሁም ሃርጌሳ አፈሳው እና አፈናው ተጥውጡፏል appeared first on Zehabesha Amharic.

↧

ሰበር ዜና: ዚወያኔ ሰላይ ኚሆላንድ ተባሚሚ!

$
0
0

ሂሩት መለሰ – ኚሮተርዳም

ሮተርዳም፣ ጥቅምት 28 ቀን 2015 – በስደት ስሙ አለማዹሁ ስንታዚው በመባል ዚሚታወቀው ዚህወሃት ሰላይ ኚኔዘርላንድስ ተባሚሚ። አለማዹሁ ስንታዚሁ ቋሚ ነዋሪ ኚነበሚበት ኚኔዘርላንድስ እንዲባሚር ዹተደሹገው በዚያ ዚሚኖሩ ኢትዮጵያውያን በኚፈቱበት ዚስለላ ክስ መሆኑም ታውቋል።

ዚሮተርዳም ኹተማ ፍርድ ቀት በአለማዹሁ ላይ ዹተመሰሹተውን ዚስለላ ክስና ማስራጃ ለሹጅም ጊዜ ሲመሚምር ኹቆዹ በኋላ ዚግለሰቡ ዚመኖርያ ፈቃድ እና ቀት እንዲነጠቅ፣ ዚሆላንድን ምድርም በአስ቞ኳይ ለቆ እንዲወጣ ውሳኔ አስተላልፏል። ኚሆላንድ ዚምመራ ቡድን እንደተሚዳነው ኹሆነ – ዚግለሰቡ ቀት ሲፈተሜ ወያኔ ዹሰጠው እውነተኛ መታወቂያ እና በርካታ ዚስለላ ሰነዶቜ ተገኝተውበታል። በእርዳታ ስም ዚተቋቋመለት ድርጅትም ተፈትሟ ማስሚጃዎቜ እንደተገኙ ለማወቅ ተቜሏል።
alemayehu-sentayehu

ይህ ሰው ትክክለኛ ስሙ ዘለቀ ፎላ ይባላል። በደርግ ጊዜ ዚኢትዮጵያ ሰራዊት አባል ሆኖ ለሹጅም አመታት አገልግሏል። ወያኔ ስልጣን ሲቆጣጠር ለፖለቲካ ተሃድሶ አዋሳ ደቡብ ጩር ቅጥር ግቢ ተላኚ። በተሃድሶ በነበሚበት ጊዜ ቁጥራ቞ው ብዙ ዹሆኑ ዚሰራዊቱ አባላትን ለወያኔ በማጋለጥ ታማኝነቱን ሲያሳይ እንደነበር ዹዚህ ዜና ዘጋቢ እማኝ ነው። ዚበርካታ ኢትዮጵያውያን ደም በእጁ ያለው አለማዹሁ ኚተሃድሶው ኚወጣ በኋላ እስራኀል ገደቡ (ዚፓልቶክ ስሙ ኢዛና) ኚተባለ ወታደር ጋር በመሆን ዹሰላም ተጓዥ ነኝ ብሎ በመገናኛ ብዙሃን ሲታይ ነበር። አለማዹሁ እና ኢዛና በዚሃገሩ እዚዞሩ ስለ አዲሱ ስርዓት መልካምነት ሲሰብኩ ኚሚሙ። ኚዚያም አስመራ ድሚስ ተልኹው ዚሻእቢያውን መሪ ኢሳያስ አፈወርቂን በወታደሩ ስም ይቅርታ ጠይቀዋል።

አለማዹሁ እና ኢዛና ለወያኔ በሰሩት ውለታ ሆላንድ ገብተው እንዲቀሩ ተደሚገ። ይህም ዚተደሚገበት ምክንያት በአውሮፓ ዚሚኖሩ ኢዮጵያውያንን ተቃዋሚ በመምሰልና በሹቀቀ መንገድ እንዲያበጣብጡና እንዲሰልሉ ነው።
በሆላንድ ሃገር ዚፖለቲካ ጥገኝነት ጠይቆ ለወያኔ ቡድን ዚስለላ ስራ መስራት ወንጀል ነው። አለማዹሁ ዚሆላንድ ዜግነት ቢኖሚው ኖሮ ቅጣቱ ዹኹፋ ይሆን እንደነበር ጉዳዩን እዚተኚታተሉ ያሉ ዹህግ ባለሙያዎቜ ተናግሚዋል።
ዹአለማዹሁ መባሚር በተሰማ ግዜ በሮተርዳም ያሉ ዚህወሃት ደጋፊዎቜ ዚአቀቱታ ደብዳቀ በመጻፍ ፊርማ ማሰባሰብ ቢጀምሩም ሊሳካላ቞ው አልቻለም። ዚአቀቱታ ደብዳቀው ግለሰቡ እዚህ ዚተወለዱ ሁለት ለጆቹን እዚመጣ እንዲጎበኝ ይፈቀድለት ዹሚል ነበር።
አለማዹሁ ስንታዚሁ ለአንዮና ለመጚሚሻ ጊዜ ኚሆላንድ ተባሚሚ። ኢዛና ግን አሁን ዹተቃዋሚ ጭንብሉን አውልቆ በግልጜ ወያኔ መሆኑን መናገር ጀምሯል። ኢዛና ዚሆላንድ ዜግነት ቢኖሚውም በሆላንድ ሃገር ስራ ሰርቶ አያውቅም። ዹቀንና ማታ ስራው በፓልቶክ ላይ ነው። ባለፈው ወር ኢትዮጵያ ዹተጓዙ ዲያስፖራ ኢንቚስተሮቜን እዚመራ በ቎ሌቭዥን መግለጫ ሲሰጥ አይተነዋል። ይህ ትርኢት ዚወያኔ ኢንቚስተሮቜ በጚበጣ እንደሚንቀሳቀሱም ያሳዚናል።

The post ሰበር ዜና: ዚወያኔ ሰላይ ኚሆላንድ ተባሚሚ! appeared first on Zehabesha Amharic.

↧
↧

በሥራ ሂደት ባለቀቶቜ ዚተጥለቀለቀቜ ብ቞ኛዋ ሀገር! –ነፃነት ዘለቀ

$
0
0

ነፃነት  ዘለቀ (ኚአዲስ አበባና ኹፊንፊኔ)

ሰሞኑን አንድ ጉዳይ ገጥሞኝ ዚወያኔውን ዚዱርዬ መንግሥት በርካታ ቢሮዎቜ ማንኳኳት ነበሚብኝ፡፡ ጉድ አዚሁላቜሁ፡፡ ዚጉድ ጉድ! ስንቱን ነግሬያቜሁ እንደምዘልቀው ግን አላውቅም፡፡ በሀገራቜን ተዝቆ ዚማያልቅ  ብዙ ጉድ እዚፈላና እዚተንተኚተኚ ነው፡፡ በአንዲት ሀገርና በአንዲት መናገሻ ኹተማ ስንት መንግሥት እንዳለም ለማወቅ ሞክሬ አልተቻለኝም፡፡ አንዱ ጋ ስትሄድ አዲስ አበባ ይልሃልፀ ሌላው ጋ ስትሄድ ፊንፊኔ ይልሃልፀ ወደ አንዱ ኀፍ ኀም ብትሄድ ደግሞ ሾገር ይልሃል፡፡ አንዱ “ወደናዝሬት ልሄድ ነው” ሲልህ ሌላው “ወደአዳማ ልሄድ ነው” ይልሃል፡፡ ስሞቜም ፖለቲካዊ ይዘት እዚተላበሱ በአጠራር ልዚነት መቀያዚምና በነገር መጓነፍ ይታያል፡፡ “እህሉ አንድ ዓይነት ሎቱ አሥራ ሁለት” ዚሆነበት ዘመን ሆኗል፡፡ ዘመነ ግርምቲ! ቧይ!! አዲስ አበባ – ፊንፊኔ፣ ናዝሬት – አዳማ፣ ደብሚ ዘይት – ቢሟቱ፣ አዋሳ – ሀዋሳ፣ ጅጅጋ -ጅግጅጋ፣ አለማያ- ሀሮማያ፣ ውጥንቅጡ ዚወጣባት ሀገር – ሰው በስያሜም ይለያያል? በስያሜና በተሰያሚ መካኚል እኮ ዚባሕርይ ግንኙነት ዚለም፡፡ ስለዚህ ሰዎቜ ለምን በዚህ ቀላል ነገር ይሻኮታሉ? በተለመደው ቢጠራ ቜግሩ ምን ይሆን? ባቢሎን በሣሎንፀ ባቢሎን በኢትዮጵያ፡፡

ወደ አንዱ ዚመንግሥት መሥሪያ ቀት ሂድ – ወግ ነውና ሲዳሩ ማልቀስ ዚወያኔ “መንግሥት”ም ያው መንግሥት መባሉ ነው እንግዲህ፡፡ እናም ስትሄድ ምን እንደሚገጥምህ ያዚሁትን ልነግርህ ነው – ተዘጋጅ፡፡

በብዙ መሥሪያ ቀቶቜ ኹዘበኛ ጀምሮ እስኚላይኛው ሥራ አስኪያጅ ወይም ሥራ አስፈጣሚ ድሚስ ዚምታገኘው ኚትግሬው ብሔር ዹተገኙ ጥቂት ዚተማሩ ወይም ሞፈር ቀምበር ሰቅለው ዚመጡ – ግን እንደኚተመኛ ዚለበሱ – ማይም ሰዎቜን ነው – ኹመደነቋቆር በስተቀር ዚማትግባባ቞ው ፍጹም ማይማን፡፡ አልፎ አልፎም ዚመሥሪያ ቀቶቜ ዚመግባቢያ ቋንቋ ዚሀገሪቱ ኩፊሮላዊ ቋንቋ አማርኛ መሆኑ ቀርቶ ትግርኛ ሆኖ ልታገኘው ትቜላለህ – ይሄ ምንም ማለት አይደለም፡፡ ይህን ያነሳሁት ለወቀሣ ሣይሆን ዚትግሬው ጠባብ ቡድን ወደ ዘጠና ሚሊዮን ዹሚገመተውን መላዋን ዚሀገሪቱን ሕዝብ በምን ያህል ብልጫ ገለባብጊ አንድን ዚመንግሥት መሥሪያ ቀት በቁጥጥሩ ሥር እንዳደሚገው ለማሳዚት ነው፡፡ እንጂ ማንም ዜጋ በፈለገው ቋንቋ ዚመግባባት መብቱ ተፈጥሯዊ እንጂ ሰብኣዊ ስጊታ እንዳይደለ እሚዳለሁ፡፡ በትግርኛቜን ዚብሔራዊ አገልግሎት ድርሻን መውሰድ ቀንቌበት ወይም ተመቅኝቌ አይደለም፡፡ ሁሉም ዹኔው ነው፡፡

መሄድ ዚነበሚብኝ መሥሪያ ቀቶቜ በውነቱ ጥቂቶቜ ነበሩ፡፡ ነገር ግን በነዚያ መሥሪያ ቀቶቜ በታዘብኩት ዹተወላገደ ሀገራዊ ምስል ምክንያት ሌሎቜ ብዙዎቜንም ጚመርኩ – ለግንዛቀዚ ስል ብቻ (just for curiosity purpose)፡፡ እናም መኚላኚያና ውጭ ጉዳይም አልቀሩኝም – ኚሃይማኖቱም ፓትርያርክ ጜ/ቀትና ምግባሚ ብልሹ ማለትም “ምግባሚ ሠናይ” ዚሚባለውን ዚኊርቶዶክስ ቀተ ክርስታን ሆስፒታልን ጭምር በሰበቡ ጎበኘሁ፡፡

አንድ ነገር ማስቀደም ፈለግሁ፡፡ በደቡብ አፍሪካ ዚአፓርታይድ ሥርዓት ኚነጮቹ ውስጥ ያን ወንድምና እህቶቻ቞ው በጥቁሮቜና በቅይጊቜ ላይ ዚዘሚጉትን ዚአፓርታይድ አገዛዝ አጥብቀው ዹሚቃወሙና ዚሚታገሉም ነበሩ፡፡ እነዚያን ዓይነት ጀናማ አእምሮ ዚነበራ቞ውና ያላ቞ው ምርጥ ዚዓለማቜን ዜጎቜ ኚዚቆሻሻ ክምሮቜ ውስጥ እያፈነገጡ ዚሚወጡበት ሁኔታ ብዙውን ጊዜ ይታያል፡፡ ዚእናት ሆድ ዥንጉርጉር መሆኑ አዲስ አይደለምና ኚወያኔም አንጀተ ብቡ እንደማይጠፋ ሁሉ ኚለዬለት ሰይጣንም ተስቶትም ቢሆን ምሕሚትን ዚሚያደርግ አይጠፋም፡፡ ዹነዚህ ዹፀሹ አፓርታይድ ነጭ ታጋዮቜ ጉዳይ ግን ለዚት ይላል፡፡ እነሱን ዹመሰሉ ፀሹ ጜዮናውያንም እንዳሉ ስንሰማ ለሰዎቜ አእምሯዊ ዕድገት ያለን አድናቆት ይጚምራል፡፡ ዚሚገርማቜሁ ነገር ዚሚጓዙበትን ብርሃን መሰል ጹለማ ዚመጚሚሻ ዕጣ ፋንታ ሲሚዱ ኹ32 እና ኹ33 ዲግሪ ዚኢሉሚናቲ ዚዕድገት ደሹጃ ሣይቀር እዚወጡ ዚጓደኞቻ቞ውን ዹቀን ቅዠት ዚሚያጋልጡና መልካም ሕይወትን መኖር ዚሚጀምሩ ደጋግ ዚቀድሞ ዚሉሲፈር እምነት አራማጆቜ አሉ፡፡ በበኩሌ ምንም እንኳን ትልቅ አደጋ ዚሚጋሚጥባ቞ው መሆናቾውን ብሚዳም በነዚህ ወደኅሊናቾው ዚሚመለሱ ሰዎቜ በጣም እደሰታለሁ፡፡ በዚህ መልክ ዹዘርም ይሁን ዚእምነት ጓዶቻ቞ውን ዹዕውር ድንብር ዹጹለማ ጉዞ እዚኚዱ ወደ እውነት ጎዳና ዚሚገቡና በስህተታ቞ው ዚሚጞጞቱ አሉ፡፡ በሀገራቜንም ዹነዚህን ዓይነት ኹጠማማ መንገድ ተመለሟቜን ቁጥር እንዲያበዛልንና ዚነፃነታቜንን ቀን እንዲያቀርብልን ፈጣሪን በጞሎት ተግተን እንወትውተው፡፡

ዚሩዋንዳን ነገር ሣልጠቅስ ማለፍ አልወድም፡፡ አክራሪ ሁቱዎቜ ቱሲዎቜን በሚጚፈጭፉበት ጊዜ ለዘብተኛ ሁቱዎቜ  ቱሲዎቜን ዚመታደግ ብዙ ታሪካዊ ሥራ ሠርተዋል፡፡ በቀታ቞ው ሞሜገው አደጋውን እንዲያልፉ ያደሚጉ ዚጀናማ አእምሮ ባለቀት ሁቱዎቜ ነበሩ፡፡ እንደጓደኞቻ቞ው ሣያብዱና ሣይወፍፉ በጭፍጹፋውም ሣይሣተፉ ለቱሲዎቜ መልካም ነገርን በማድሚግ አሁን ላለው አንጻራዊ ሰላም ዚበቁ፣ በዚያም ምክንያት ኅሊናቾውን በደም ታሪክ ያላጚቀዩ ሁቱዎቜ አሉፀ ለደግ አሳቢ አእምሮ ምሥጋና ይድሚሰው፡፡ ሁሉም ያልፋልፀ ዚማያልፍ ነገር ቢኖር ኖሮ ቁጭት ንዎታቜን ወሰን ባልተገኘለት፡፡

ኹፍ ሲል ያልሁትን ያልሁት አለምክንያት አይደለም፡፡ ደጋግ ትግሬዎቜ አለን፡፡ ኹነፈሰው ጋር ዚማንነፍስና በወገኖቻቜን መገፋትና መሳደድ/መሰደድ ዚምንኚፋ፣ ዚምንበሳጭና ዹምንቆጭ ጥሩ ጥሩ ትግሬዎቜ አለን፡፡ አላህ ጚርሶ አይበድልም፡፡ ኚንፍሮም ጥሬ ይወጣል፡፡ እናም ጥቂቶቜም ቢሆኑ በአሁኑ ሞውራራ ዚትግሬ አገዛዝ አንጀታ቞ው ዚሚያርር በዚህም ምክንያት ዹዘር ሐሹጋቾው ያመጣውን ሀገራዊ መቅሰፍት ለመንቀል ኚጭቁኖቜ ጋር ለመታገል ዚቆሚጡ አሉ፡፡ ትግላ቞ው እስኚሞት ዚሚያደርስ መሆኑን እያወቁ ለኅሊናቾው ሲሉ ኹመኹሹኛው ሕዝብ ጎን ተሠልፈው ዹሚዋደቁ እነአብርሃ ደስታና አሥራት አብርሃም፣ አብርሃም በላይ – እንዎት ነገሩ ይሄ አብርሃ ዚሚሉት ስም 
 ብቻ ጥቂት ዚማይባሉ ትግሬዎቜ አሉን፡፡ ጌታ ጥሎ አይጥልም፡፡ ጥቂትም ቢሆኑ ዚመኚራ ገፈታቜንን ዚሚጋሩ ትግሬዎቜ መኖራ቞ው ሞክማቜንን ዚሚጋራን ኚመኖሩ አኳያ መጠነኛ እፎይታ ይሰማናል፡፡ በተሹፈ ተኚድኖ ይብሰል፡፡ ለዛሬ ግን ለምን ይኹደናል? ያዚሁትን እዘኚዝኚዋለሁ፡፡

በዬመሥሪያ ቀቱ ኃላፊውም ዘበኛውም ጜዳቱም ትግሬ ነው፡፡ ለይስሙላ ቢሮ ተቀምጩ ዹሚገኘውን ኃይለ ማርያም ደሳለኝን ዹመሰለ መናጆና “ሲጠሩት አቀት፣ ሲልኩት ወዎት” ባዩን ዜጋ ታዲያ ኹቁም ነገር እንዳትቆጥሩት – አንድም ሥልጣን ዹሌለው በዓይን ጥቅሻና በቀጭኒቱ ሜቊ ኚትግሬዎቜ መንደር ዚሚታዘዝ መጋጃ ነው፡፡ ይህ በጣም ግልጜ ነው፡፡  ወ/ሮ ትብለፅ ጎይታይ – ዹሰው ኃይል አስተዳደር ዚሥራ ሂደት ባለቀት፣ አቶ መሓሪ ሜኑን – ዚወጪና ገቢ ቁጥጥር ዚሥራ ሂደት ባለቀትፀ ዶክተር ሐጎስ ዕንቋይ – ዚአማራ ክልላዊ መንግሥት ዕንባ ጠባቂ ዚሥራ ሂደት ባለቀት፣ አቶ ዘርዑ መዓሟ – ዚደቡብ ሕዝቊቜ ክልል ዚመሬት ድልድል ዚሥራ ሂደት ባለቀትፀ ወ/ሮ ሐሹጓ ግደይ – ዚአዲስ አበባ ሎቶቜ ሊግ ሰብሳቢፀ ወጣት አሹጋዊ አስገዶም – ዚአዲስ አበባ ወጣቶቜ ሊግ ዹዘርፍ ሰብሳቢፀ እማሆይ አብሚኞት ፍትዊ ዚኪዳነ ምሕሚት ገዳም እመምኔትፀ አባ ናትናኀል ኪሮስ ዹአ.አ ሀገሹ ስብኚት ሥራ አስኪያጅፀ አቡነ ናትናኀል ዚኊርቶደክስ ቀተ ክርስቲያን ፓትርያርክና  አቶ ማለትም ዶክተር ኃይለሚካኀል ጎይቶም ዚሲቪል ሰርቪስ ዩኒቚርስቲ ዚዕድሜ ልክ ፕሬዝደንትና በወያኔ ማዕኹላዊ ጜ/ቀት ዚሙስና ማቀላጠፊያ ዘርፍ  ዚሥራ ሂደት ባለቀት 
 አይ! ያሣፍራል፡፡ አንዳርጋ቞ው ያቺን ስድ ሎት በተመለኹተ ሲናገር ዹአማርኛውን “ያሞማቅቀኛል” ዹሚለውን ቃል በስሜታዊነት ዘንግቶት በእንግሊዝኛው “cringe” አደርጋለሁ ብሎ ነበር፡፡ እኔም በዚህ ዚትግሬው ገዢ መደብ ክሪንጅ አደሹግሁ – ተሳቀቅሁለት – ተሞማቀቅሁላ቞ው፡፡ አንጎል ምን ያህል ቢጠፋ ዚዚህቜን ቀመር ዹኋላ ጊስ እንዎት ያጧታል? እንዎ! ኚታቜ እስኚ ላይ በትግሬ አስይዘህ ስታበቃ፣ ሌላውን ዜጋ እንደባይተዋር ወርውሹህ ስታበቃ፣ ሌላውን ዜጋ በተለይም አማርኛ ተናጋሪውን ጹፍጭፈህና አስጚፍጭፈህ ንቀህና አዋርደህ ኚሀገሩ ጉዳይም አግልለህ ዚትሚናውን ጥለህ ስታበቃ፣ 
 በዚህ በተደናበሹ አገዛዝ ስንት ዓመት ትኖራለህ? ዚአንዲን ቃል ልድገመው – ተሞማቀቅሁላ቞ው፡፡ እኔ ያፈርሁት በነሱ ነው፡፡ ማይምነት ለካንስ እስኚዚህን ያጋልጣል? ሱቅ ውስጥ እንደገባ ሕጻን ሁሉ ነገር ዐይን ዐዋጅ ሆነባ቞ውና ተጚነቁ፡፡

ትግሬዎቹ ዚተማሩ ቢሆኑና ለቊታው ቢመጥኑ ለኔ ጉዳዚ አይደለም፡፡ ምክንያቱም ለቊታው ዚሚመጥን ሰው ኹሆነ ትክክለኛ አገልግሎት ይሰጣልና ዚሚበሳጭና ዚሚናደድ ተስተናጋጅ አይኖርም፡፡ እነሱ ግን ምኑንም ስለማያውቁት በዘር ብቻ እዚተጠራሩ ሀገሪቱን ዚጚሚባ ተዝካር አድርገዋታል፡፡ ዚአምስተኛ ክፍል ጄኔራልና ዚአሥሚኛ ክፍል ዶክተር ባለሥልጣን ባለባት ሀገር – ዚመካኚለኛና ዝቅተኛ ቢሮዎቜ ባለሥልጣናት እስኚምን ድሚስ ሊማሩ እንደሚቜሉ ይታያቜሁ፡፡ ሀገሪቱን ኚዳር እዳር እዚተጫወቱባት እኮ ነው፡፡ ኧሹ ጓዶቜ ፍጠኑና ይህቜን ሀገር ኹዚህ አሹንቋ በቶሎ እናውጣት ማለትም አውጧት፡፡

በዚቀበሌዎቜና ወሚዳዎቜም ሄጃለሁ፡፡ ሁሉም ቊታ አዛዥ ናዛዡ ትግሬ ነውፀ ልብ አድርጉ – ዹሌላ ዘውግ ተሹዋሚ ዹለም እያልኩ አይደለም – ሞልቷል፡፡ ግን ራሱን ቜሎ አይሠራም – ኚጥቃቅን ነገሮቜ በስተቀር፡፡ ኩነግ ወይም ኚወሮቜ አንድኛው እንዳይለጠፍበት በመስጋት ሁሉም ዹሌላ ብሔር “ሹም” ክፉኛ እዚተሳቀቀ ነው ሥራ ውሎ ዚሚገባው፡፡ በተሹፈ ዚትግሬው ባለሥልጠን ደሚቱን ነፍቶ ሲነፈርርና በሥነ ልቩናዊ ዚበላይነት እርካታ ሲንጎማለል ታያዩታላቜሁ፡፡

ባይገርማቜሁ ዚዛሬ ሁለት ዓመት አሥሚኛ ክፍልን ማለፍ ያቃተው አንድ ወጣት ትግሬ አሁን ዚአንድ ወሚዳ ሥራ አስፈጻሚ ነው፡፡ ኹሞላ ጎደል ሁሉም ተሹዋሚ ትግሬ በቜሎታውና በትምህርቱ ሣይሆን በዘውጋዊ ቀሚቀታው ነው፡፡ ዚቀሚቀታው ልክ ደግሞ ኚትግሬም ትግሬ እዚተማሚጠ ነው፡፡ ቅድሚያ አድዋ፣ ቀጥሎ ሜሬ፣ ቀጥሎ አክሱም 
 ዓይነት እጅግ ዹወሹደ ጎጠኝነትና መንደርተኝነት፡፡ በትምህርትና በቜሎታ መመደብማ ለይቶለት ገደል ኚገባ ሃያ አራት ዓመታትን ሊያስቆጥር ጥቂት ወራት ብቻ ቀርተዋል፡፡ መለስ – ባለበት ሲያስመልሰው ውሎ ይደርና –  በሕይወት እያለ ለፖለቲካው እስኚታመነ ድሚስ ዘበኛንም ሚኒስትር ማድሚግ እንደሚቻል በኩራት ተናግሮ ነበር፡፡ ለንግግርም ለኚት ዹሌላቾው እንዎት ያሉ ባለጌዎቜ ናቾው እኮ! ፈጣሪን ምን ቢበድሉት ይሆን እንዲህ አበለሻሜቶ ዚፈጠራ቞ው? እኛስ ብንሆን ኃጢኣታቜን ምን ያህል ኚተራራ ቢገዝፍ ይሆን ካልጠፋ አምባገነን እነዚህን ዹመሰሉ ዚሲዖል ትሎቜ ዹሰጠን? እስኪ ቁጭ ብላቜሁ አስቡት፡፡ ሀሁንና ኀቢሲዲን ባልቆጠሩ ማይማን እንዎት ሀገር ትተዳደር? ምን ዓይነት ውርጅብኝ ነው? በስማም!

ጭንቀቮን ልናገር፡፡ አሁን በትግሬ ወያኔ ኹላይ እስኚታቜ ዚተጥለቀለቀውን ዚሀገሪቱን ቢሮክራሲ ነገ ነፃ ስንወጣ እንዎት አድርገን ነው ዚምናስተካክለው? ማን ነው ወንዱ ይህን ሁሉ በትግሬ ዹተጹናነቀ መሥሪያ ቀት ሁሉ አስተካክሎ እውነተኛ ዹሁሉም ብሄሮቜ ዚተማሩ አባላት በውድድር አልፈው ሀገሪቷን እንዲመሩ ዚሚያደርግ? በጣም ኚባድ ዚቀት ሥራ ተጎልቶላቜኋል፡፡ መለኮታዊ ጣልቃ ገብነት ካልታኚለበት ኚሆድና ኚዘሚኝነት ዚቀት ጣጣ በስተቀር አንድም ዕውቀት ዹሌለውን ይህን ዚወያኔ መንጋ በሠለጠነና በተማሹ ኃይል ለመተካት ትልቅ ቜግር ይገጥማቜኋል – እናንት ኢትዮጵያውያን፡፡ እኔ ኢትዮጵያ ነፃ በወጣቜ ማግሥት ይህን ጉድ ላለማዚት እግሬ ባወጣኝ  ኚሀገሬ ዚምሰደድ ይመስለኛል፡፡ እፈራለሁ፡፡ አሁን ያለው ሁኔታ በጣም ያስፈራል፡፡ ሁሉም በአንድ ብሔር ይያዝ? አደገኛ መቅሰፍት ነው! ዹሚገርምህ ሌላ ነገር – ወያኔ ኹሆንክ ዹፈለገውን ዓይነት ዚአካል ጉድለት ቢኖርብህ ኚሥራህ ዚሚያነቃንቅህ ዚለም፡፡ ጣቶቜ ዚሌሉት ፖሊስ፣ እጅግ እግር ዹሌለው (በአርትፊሻል ዚሚንቀሳቀስ) ዚጥበቃ አባል ታገኛለህ፡፡ ዚትግሬነት ማንነት ብዙ ምናልባትም ሁሉንም ህጎቜ ይደፈጥጥልሃልፀ በዚህ ዓይነት ሁኔታ ዘሚኝነት በምንም ዓይነት ምድራዊ ህግ ዹሚገዛ አይመስለኝም፡፡ ህግ ዚሚሠራው ለሌሎቜ እንጂ ለወያኔ አይደለም፡፡ ይህም በጣም አሣፋሪ ነው፡፡ ኹህግ ውጪ ይነግዳሉፀ ኹህግ ውጭ ያመርታሉፀ ኹህግ ውጪ ያኚፋፍላሉፀ ኹህግ ውጪ ዹሀገርን ሀብት ይቀራመታሉፀ ኹህግ ውጪ ያስገባሉፀ ኹህግ ውጪ ያስወጣሉፀ ኹህግ ውጪ ይጠቃቀማሉፀ ኹህግ ውጪ ሌሎቜን ያፈናቅላሉፀ ኹህግ ውጪ ዚፈለጉትን ቊታ አጥሚው ይይዛሉ – ይሞጣሉ- ይለውጣሉፀ ኹህግ ውጪ – ኹፈለጉ ላይመልሱ ጭምር –  ኚባንክ ይበደራሉፀኚህግ ውጪ ያሻ቞ውን ሁሉ አላንዳቜ ማመንታት ይፈጜማሉ፡፡ እነሱ ህግና እግዜር ሆነዋል – ኧሹ ኚማያውቁት እግዜሩም በላይ፡፡ እኛን ምሥኪኖቹን ምን ይዋጠን?

ሌሎቜ ዜጎቜን ስታዩዋ቞ው አንጀታቜሁን ይበሉታል፡፡ ሀገሪቱ በአንድ ብሄር ቁጥጥር ሥር እንደመዋሏ ሌሎቜ ዚቀላዋጭነት ጠባይ ይታይባ቞ዋል – ሀገሪቱ ዚነሱም እንዳልሆነቜና ባይተዋር ዹመሆናቾውን ጉዳይ ሳይወዱ በግዳ቞ው እንዳመኑ ያህል ትሚዳላቜሁ – ኚሁኔታ቞ው፡፡ ለበርካታ ዓመታት በቅልውጥናና በማጎብደድ መኖር ዚበታቜነት ስብዕናን ሣያዳብር ዹሚቀር አይመስለኝም – ስለሆነም ኢትዮጵያውያንን ኹዚህ አገዛዝ ነፃ አውጥቶ ዚራሳ቞ውን ሰብኣዊና ብሔራዊ ማንነት እንደገና ለማላበስ ኹፍተኛ ትግል ሣያስፈልግ አይቀርም፡፡ በዚመሥሪያ ቀቱ እንደልቡ ሲደነፋና ሌሎቜን እያንጓጠጠና እያላገጠባ቞ው ሲያዝ ዚምታዩት ትግሬ ነው – ባለጌው ዚሕወሓት ጀሌ ማለቮ ነው፡፡ ሌላውማ እንደኔው አክስትና አጎት በልመና አዲስ አበባን እያጥለቀለቀ ነው፡፡ ግራ ዚተጋባ ነገር ነው ዚገጠመን፡፡ ማጣፊያው ያጠሚን ግራ መጋባት፡፡ ቁጭ ብለን ዹሰቀልነውን ቆመን ማውሚድ ያቃተን ትልቅ አደጋ፡፡

ትግሬ ያልሆነ ዚይስሙላው ባሥልጣን ለምሳሌ ጜዳቷ ቢሮውን ለማጜዳት ብትገባ ልታዘው ዚመጣቜ መስሎት ዚሚያሞሚግድላት አይጠፋም – ትግሬ በመሆኗ ብቻፀ በራስ ዹመተማመን ነገር ኚብዙዎቜ ዜጎቜ ሙልጭ ብሎ ጠፍቷልፀ ፍርሀት ነግሊአል፡፡ በዚቊታው ዚሚታዚው ዚሌሎቜ ወገኖቜ መሳቀቅ በአንዲት ሀገር ዚተለያዬ ዜግነት መኖርን ያመላክታቜኋል፡፡ “ለካንስ አእምሯዊ ዚዕድገት ደሹጃውን ባልጚሚሰ ሰው መገዛት እጅግ ኚባድና አዋራጅም ነው” ብላቜሁ ትተክዛላቜሁ – ልክ እንደኔ፡፡ በዚሄድኩበት ቊታ ሁሉ በሀፍሚት እዚተሞማቀቅሁ እመለሳለሁ፡፡ ደግሞም ዹሚኹሹፋኝ ነገር አለ፡፡ በቃ – ቢሮውም፣ ሕንፃውም፣ ምኑም ምናምኑም እንዳንዳቜ ነገር ይሾተኛል – እጅግ ዹሚቀሹናና ዹሚኹሹፋ ሜታ፡፡ ዚሜታው መንስኀ እንደሚመስለኝ ማይምነቱ፣ ዘሚኝነቱ፣ መድሎው፣ በዚሥፍራው ዚሚታዚው ዚማስመሰል፣ ዚመዋሞትና በግልጜ ዹማጭበርበር ወያኔዊ ባሕርይ በድምሩ ዚፈጠሩት ግማት ነው፡፡ ዚመሥሪያ ቀቱ ጋጋታ፣ ዚሥራ ሂደቶቹና ንዑስ ዚሥራ ሂደቶቹ ብዛት፣ ዚሥራ ፈት “ሠራተኛ”ው መርመስመስ፣ ዚ቎ሌቪዥኑና ዚጋዜጣው ዐይን ያወጣ ቅጥፈትና ዕብለት፣ ዚውሞቱ ምርጫ ዚማታለልና ሕዝብን ዹማነሁለል ሂደት፣ ዘገምተኛ ዜጎቜን ሣይቀር ያጡ ዚነጡ ድሆቜን በካድሬነት መልምሎ በማሠማራት በሕዝብ ላይ ዹሚደሹገው ወኚባ 
 ሲታይ ሀገር በነሲብ እዚተነዳቜ እንደሆነ ግልጜ ይሆንላቜኋል፡፡ ኚምርጫ ውጪ ሌላ ዜማ ዚለምፀ ነፃና ፍትሃዊ ምርጫ ዚሚያካሂዱ ይመስል በም..ር..ጫ(በትግርኛ ሥልት አንብቧት) ወሬ ናውዘዋል – ዚማያውቁትን ምርጫ፡፡ በዚሚኒስትር መሥሪያ ቀቱ ትርምስ ነው፡፡ እዚህም እዚያም ውክቢያ ነው፡፡ መርመስመስ ነው፡፡ ለቀልድ በተቋቋመ ዚሚንስትር መሥሪያ ቀት ውስጥ አንድ ሚኒስትር ሊስትና አራት ሚኒስትር ዎታ፣ ሃያና ሠላሣ ዋና ዚሥራ ሂደት ባለቀቶቜ 
 ቅብጥርስ ቅብጥርስ፡፡ ግን ሁሉም ኚንቱ፡፡ ጠብ ዹሚል ነገር ዚለም፡፡ ሁሌ ቁልቁል፡፡ ዚመፈክሩ ዓይነት አበዛዙ
 ሙስና ዚዕደገት ፀር ነው 
 እንደጀመርነው እንጚርሰዋለን 
 ራዕይህን ኚግብ እናደርሳለን 
 አንተ ብትለዚንም ራዕይህና ውድ ባለቀትህ አዜቢና ኹኛ ጋር ናቾው(ኚራሎው ምርቃት ጋር)ፀ ኚሊስት ዓመታት በላይ ዹወሰደ በዚትም ሀገር ያልታዬ ሀዘን – በዚህስ ሰሜን ኮሪያም ሳትበልጠን አትቀርም – ወዲያው ነው ዚሚሱት ዚነኪምን ሞት፡፡ ዚባልና ሚስት ወይም ዚልጅ፣ ዚወንድምና ዚእህት ሞት እንኳን በስድስት ወርና በዓመት ይሚሳል፡፡ ሕይወት በዹፈርጁ ነውፀ ዹሞተ ይሚሳል -ያልሞተ ኑሮውን ይቀጥላል፡፡ በሞተ ሰው ምክንያት ሕይወት ቀጥ አትልም – እንደኢትዮጵያፀ እኛ ኚመለስ ሞት በፊት እንደነበርነው ቀጥ ብለን አለን – እንዲያውም ብሶብን፡፡ በሞተ ማላዘን ዚጀናማነት ምልክት አይደለም፡፡ ደግሞም ብዙዎቹ መለስን ኚልባው ወደውት አይመስለኝም – ለማስመሰል ነው፡፡ እንደታዘብኩት በርሱ ስም ልጁን ዚሚጠራ እንኳን አልገጠመኝም፡፡ ይህ በራሱ ዚሚያሳዚው እርሱን ዚወደዱት ለጥቅማ቞ው እንጂ ማፈሪያቱን እንደማይክዱት ነው፡፡

ደግሞም
 ዹዓላማና ግቡ ዝርዝር 
 ዹዚህ ሚኒስትር መ/ቀት ራዕይ 
. ዓላማዎቜ 
. ግብ 
. ዚሥነ ምግባር መርሆዎቜ 
 ታማኝነት፣ ግልጜነት፣ ሃቀኝነት፣ ተጠያቂነት፣ ቅንነት፣ ለሕዝብ ታዛዥነት፣ 
 አቀት አቀት ዹሚነበበው ጉድ! በተግባር ግን ሁሉም ኚዜሮ በታቜ፡፡ መጥኔ ለኢትዮጵያና ለኢትዮጵያውያን! ሶማሌና ጂቡቲ በስንት ጣማ቞ው! ምነው ጂቡቲያዊ ወይም ፊጂያዊ ወይንም ዶሞ ሃይቲያዊ ሆኜ በተፈጠርኩ ኖሮ፡፡

ለማንኛውም ዚቀ቎ን ዹሰሞኑን አዲስ ሹመት ልግለጜላቜሁና ልሰናበት፡፡ መቌም ጊዜው ዚቀልድ ሆኗል፡፡ ዚቀተሰቀ አባላት ለጊዜውና ለአሁኑ ስድስት እንደሆኑ ይታወስልኝ – ቡቜዬንና ውርዹን ጚምሮ፡፡

 

በህገ መንግሥታቜን አንቀጜ 39 መሠሚት ዚነፃነት ዘለቀ ቀት አዲሱ ዚሥልጣን መዋቅር

 

ዶክተር ነፃነት ዘለቀ

ዚቀቱ ዹውጭ ጉዳዮቜ ዚሥራ ሂደት ባለቀት

ሚዳት ፕሮፌሰር ሞዋርካብሜ እርገጀ

ዚቀቱ ዚቀት እመቀትነት ጉዳዮቜ ዚሥራ ሂደት ባለቀት

 

ወጣት ዘገዹ ነፃነት (ወንድ ነው)

ዚቀቱ ፀሹ-ኢሣት አባላትን ዚማብዛትና ፎክስሙቪስን ዹማዘውተር ንዑስ ዚሥራ ሂደት ባለቀት

 

ሕጻን ደምመላሜ ነፃነት

ዚቀቱ ዚሞሰብና ድስት ጉዳዮቜ ንዑስ ዚሥራ ሂደት ባለቀት

 

ቜሎማደር (ቡቺ)

ዚግቢው ፀጥታና ደኅንነት ጉዳዮቜ ዚሥራ ሂደት ባለቀት

በድምጜሜ ይራዱ (ውርዬ)

ዚቀቱ ሞሰብ ገልብጥ ዐይጊቜን አባራሪ ግብሚ ኃይል ዚሥራ ሂደት ባለቀት

 

ማሳሰቢያ፡- ይሄ አበበ ገላው ዚተባለ ልጅ ነገር መፈልፈል ይዟልና ለርሱ ሞር ላለመመ቞ት ስል              ዹኔን ዚዶክትሬት ማዕሹግ ያገኘሁት እንደወያኔዎቹ ኚሎን቞ሪ ዩንቚርስቲና ኚመሳሰሉት           ዲግሪ ቞ብቻቢዎቜ በዶላር ገዝቌ ሣይሆን በላቀና በጥሚ቎ በቀተሰብ ጉባኀ ዹተሰጠኝ            መሆኑን እንዲሁም ክብርት ባለቀ቎ በሆም ኢኮኖሚክስ ዹሹ/ፕሮፌሰርነትን ማዕሹግ ኹዚሁ       ቀተሰባቜን ያገኘቜ መሆኗን ልገልጜ እፈልጋለሁ(አይ ዚምትጠምቀው ጠላ – ዚዶሮ ዐይን              ይመስላል፡፡)

ዘግይቶ ዹደሹሰኝ አዝናኝ ወሬ!

ዚወያኔ ዚምርጫ ቡቜሎቜ እንዲህ አደሹጉ አሉ፡፡ በዚያን ሰሞን ደብሚ ዘይት አካባቢ ዚምግብ ዘይትን ኚዚሱቁ ያጠፋሉ፡፡ ኚዚያም ሕዝቡ ሲንጫጫ በዹቀበሌው ያመጡና ሕዝቡ ወደነዚያ ቀበሌዎቜ በመሄድ ዘይት እንዲገዛ ያስነግራሉ፡፡ ነዋሪው ወደዹቀበሌው ሲሄድ ግን “ዚምርጫ ካርድ ዚማይወስድ ዘይት አይሰሞጥለትም” ይሉና በግድ ካርድ ያስወስዳሉ፡፡ ይቺ ናት ምርጫ፡፡ ሕዝብን እያስራብክና በመሠሚታዊ ፍላጎቱ እዚመጣህ ምርጫ ካርድ እንዲወስድ ማስገደድ፡፡ ኚዚያም በኮሮጆ ገልባጭ ልዩ ኃይል ዚሕዝብን ካርድ ለወያኔ ማዛወር፡፡ ኚዚያም ዹግፍ አገዛዝህን መቀጠል፡፡ ቀልደኞቹ ዚወያኔ ዚምርጫ አስፈጻሚ ካድሬዎቜ ልክ ይሕዋ ምሥክሮቜ     ይቺን ጜሑፍ አይተዋታል?” እያሉ ሃይማታውን ለማስፋፋት እንደሚሞክሩት ዚወያኔ ጭፍሮቜም በዚመንገዱና በዚጥጋጥጉ በዚመውጫና መግቢያ በሮ቞ እዚጠበቁ “ዚምርጫ ካርድ ወስደሃል?” እያሉ ሲያሰለቹ ብታዩ ደግሞ አዲስ ሃይማኖት ተመሠሹተ ወይ ትላላቜሁ፡፡ ዚጉድ ሀገር፡፡ አፉን ኹፍ በሚውል ዚምርጫ ካርድ መውሰጃ ጣቢያ ስንትና ስንት ሚሊዮን ሕዝብ መመዝገቡን ስንሰማ ዚወያኔውን ውሞት ለኚት ዚለሜነት እንሚዳለን፡፡ በ97 ያ ሁሉ ሕዝብ ተመዝግቩ 26 ሚሊዮን ነበር ዚተባለው – እርግጥ ነው ያ ቁጥር እውነትም ሊሆን ይቜላል፡፡ በቀጣዩ ዹ2002 “ምርጫ” ግን ጥቂት መቶ ሺዎቜን መዝግበው ሲያበቁ በሀገሪቱ 32 ሚሊዮን መራጭ እንደተመዘገበ ቅንጣት ሣያፍሩ በሚዲያ቞ው ለፈፉ፡፡ ቁጥር ዚሚያውቁ አይመስሉኝም እነዚህ ደነዝ ወያኔዎቜ፡፡ ኹሁሉም ዹበደላቾው እርጉሞቜ፡፡

comment_stage_5

 

 

 

The post በሥራ ሂደት ባለቀቶቜ ዚተጥለቀለቀቜ ብ቞ኛዋ ሀገር! – ነፃነት ዘለቀ appeared first on Zehabesha Amharic.

↧

ዹ 119ኛው ዝክሹ አድዋ ፀ 1888   –ኹበደ አገኘሁ ቩጋለ

$
0
0

Battle of Adwaዚተኚበራቜሁ አባቶቜ ፥ እናቶቜ፥ ወንድሞቜ፥ እህቶቜና ልጆቜ ! ዛሬ በዚህ ዚተሰባሰብነው ጀግኖቜ አባቶቻቜንና እናቶቻቜን ዚዛሬ 119 ዓመት እንደዛሬው በነገድ ወይምብ ብሔር እንዲሁም በሃይማኖት ሳይኚፋፈሉ ፥ ለአንድ ብ቞ኛ ዓላማ በአንድነት ተሰልፈው ባህላ቞ውን ፀ ሃይማኖታ቞ውንፀ ታሪካ቞ውንፀ ሰብአዊና ብሔራዊ ነፃነታ቞ውንፀ ባጠቃላይ ኢትዮጵያዊ ማንነታ቞ውን አጥፍቶ ዹቅኝ ተገዥ ባርያ አድርጎ ለመግዛት ኹአህጉሹ አውሮፓ ተንቀሳቅሶ፥ ባህሚ ኢያሪኮንና ቀይ ባሕርን ተሻግሮ፥ ዚእናት አገራቜንን ክብሚ ወሰን ጥሶ ዚገባውን ዚጣልያን ወራሪ ዚጠላት ጩር አይቀጡ ቅጣት ቀጥተው ለመጀመሪያ ጊዜ ዚአፍሪካ ጥቁር ሕዝቊቜ በአውሮፓውያን ቅኝ ገዥዎቜ ላይ ድል ተቀዳጅተው በዓለም ታሪክ ውስጥ ታላቅ ምዕራፍ ያስመዘገቡትን ታሪካዊ ዕለት እኛ ዹልጅ ልጆቻ቞ው በኩራት ለማስታወስ ነው ። ይህ ጀግኖቜ አባቶቻቜንና እናቶቻቜን ደማቾውን ቀለም አጥንታ቞ውን ብዕር አድርገው ያስመዘገቡት ታላቁ ዚታሪክ መዝገብ ዚተመዘገበበት ዕለት፥ እሑድ ዕለተ ሰንበት ፥ ዚካቲት 23 ቀን 1888 ዓ.ም ነበር።

ለመሆኑ ዚጊርነቱ መንስኀ ምን ነበር ?

አውሮፓንን ያጥለቀለቀው ዹ19ኛው ምእት ዓመት ዘመናዊ ዚእንዱስትሪ ለወጥ ወይም እንዳስትርያል ሪቮሉሺን ለእንዳስትሪያ቞ው ጥሬ ዕቃ፥ ማለት እንደማዕድን ዚመሳሰሉትን ሀብተ ኹርሠ ምድሮቜ እንዲፈልጉ አውሮፓውያኑን አስገደዳ቞ው። ስለዚህ ዘመናዊ እንዳስትሪ ባስገኘላ቞ው ዘመናዊ ዹጩር መሳርያ አውሮፓዊ ያልሆነ ዘር ዚማይኖርባ቞ውን ዚአፍሪካንና ዹ እስያን ፀ ቀደም ብለውም ዹሰሜንና ዚደቡብ አሜሪካን ነባር ሕዝቊቜ እዚጚፈጚፉ በቁጥጥራ቞ው ስር አደሚጉ።ዚፈለጉትን ጥሬ እቃም በነፃ ማጋዝ ፀ ያመሚቱትን ሞቀጥም በቅኝ በሚገዟቾው አገር ሕዝቊቜ ላይ በማጋሹፍ ካፒታሊዝምን ገነቡ። በቅኝ ዹሚገዟቾውን ሕዝቊቜ ነባር ኃይማኖታ቞ውን፣ ቋንቋዋቾውንና ታሪካ቞ውን ለወጡት። ዚስነ መንግሥት፥ ዚምጣኔ ሀብት፥ ዚማኅበራዊ ኑሮ ነፃነታ቞ውንና ሰብአዊ ክብራ቞ውን ገፈፉት። ስነ ልቩናቾውን በመቀዹር በራሳ቞ው እንደሰው  ዹመተማመን ባህርያ቞ውን እንዲያጡ በማድሚግ ዚበታቜነት ስሜት እንዲያድርባ቞ው አደሚጉ። ባጠቃልይ በቃላት ለመግለጜ ዚሚያስ቞ግር ኢሰብአዊ ድርጊት ዚሚፈጜሙበት ዘመን ነበር። ይህን በመሰለው ዹዓለም ተጚባጭ ሁኔታ ፥ አውሮፓዊ ያልሆነ ሕዝብ ፥ በተለይም ጥቁር አፍሪካዊ ሕዝብ ሁኖ ለአውሮፓውያን ነጮቜ አልገዛም ፣ ክብሚወሰኔንና ሰብአዊ ክብሬን አላስደፍርም ብሎ ለውጊያ መሰለፍ ዹማይሞኹር እርምጃ ነበር። ዘመኑ ነጮቜ ነጭ ያልሆነውን ሕዝብ ነፃነት መግፈፍ ኹላይ ኚአዶናይ (ኹአምላክ) ዚተሠጣ቞ው ሥልጣን አድርገው ይቆጥሩት ነበር።ለዚህ አላማቾውም ‘ዚሞራል ዚበላይነት አለን ‘ ይሉ ዚነበሩት ምስዮኖቻ቞ው በክርስትና ስም  “ዚቄሣርን ለቄሣር ፥ ዚእግዚአብሔርን ለእግዚአብሔር አድርግ ” ዚተባለውን መለኮታዊ ትእዛዝ ጥሰው ዚቄሣራውያን መሳርያ ሁነው ኚክርስትና እምነት ጋር ዹተቃሹነ ዹግፍ ተልእኮ ይፈጜሙና ያስፈጜሙ ነበር። በክርስትና ስም ዹተፈጾመውን ባርባራ ኪንግሶልበር ዚተባሉ አሜሪካዊት “ ዘ ፖይዝን ውድ ባይብል” በተባለው ታሪካዊ ልብ ወለድ መጜሐፋ቞ው በሰፊው ገልጞውታል። ፖፕ ዮሐንስ ጳውሎስ 2ኛም ይህን በሚመለኚት ዚዛሬ 18 ዓመት አካባቢ በዘመኑ በክርስትና ስም ግፍ ለተፈጞመባ቞ው ሕዝቊቜ ይቅርታ ጠይቀውበታል።

አውሮፓውያን በዚህ መልክ በተለይም በአፍሪካ ሕዝቊቜ ላይ ይህን ግፍ ሲፈጜሙበት በነበሚበት ዘመን አገራቜን ኢትዮጵያ ለዚህ አይነት ዚነጮቜ ግፍ ሰለባ ባትሆንም በራሷ ልጆቜ በመሳፍንት አገዛዝ ተኹፋፍላና በእርስ በርስ ጊርነት ተዳክማ ነበር። በዚህም ምክንያት ማዕኹላዊ መንግሥቷ መኖሩና አለመኖሩ ለውጭ ኃይሎቜ አጠራታሪ ነበር። በዚህ ሁኔታ እንግሊዞቜ በ1797 ዓ.ም. ምጜዋ ላይ ሰፈሩ። ነገር ግን አካባቢው ያኔ በራስ ሚካኀል ስዑልና ማዕኹላዊ መንግሥቱን ወክለው በነበሩት በጎንደር ነገሥታት ቁጥጥር ሥር እንደነብር በሚገባ ዚሚያሚጋግጡ ዚታሪክ መሚጃዎቜ ኣሉን። ይህ በዚህ እንዳለ ፥ በ1846 ዓ.ም ጀምሹው ቆላማውን ዚባህሚ ነጋሺ አካባቢ ግብጟቜ ሰፍሚውበት ነበር። ኚዚያም አንድ ዹግል ንብሚት ዹነበሹ ዚኢጣልያ ዚባህር ጭነት ማጓጓዥያ ኩባንያ አሰብን ኚአካባቢው መስፍን (ሡልጣን) በ1874 ዓ.ም ገዛው። በመቀጠልም ኹ3 ዓመት በኋላ በእንግሊዞቜ አበሚታቜነት በ1877 ዓ.ም ዚኢጣልያ ሠራዊት ምጜዋ ላይ ሠፈሚ። በዚህም ወቅት ግብጜም በበኩሏ በዚህ አካባቢና በሃሹር በኩል ክብሚ ወሰናቜን ደፍራብን ነበር።

ይህን በመሰለ ሁኔታ አገራቜን ኢትዮጵያ ኚአድዋ ጊርነት በፊት ለ20 ዓመታት ያለ እሚፍት ኹውጭ ጠላቶቜ ጋር ክብሚ ወሰኗንና ብሔራዊ ነፃነቷን ለመጠበቅ ስትታገል መቆዚቷ ይታወሳል። ለዚህ ታላቅ ብሔራዊ ነፃነትና ማንነት ጥበቃ ጀግኖቜ መሪዎቿም መስዋዕት ሁነዋል። ኚተሰውት መሪዎቜ መካኚል ሁለቱን እንጥቀስ። ዘመነ መሳፍንትን አጥፍተው ዘመናዊትና አሐዳዊት ኢትዮጵያን ዚመሠሚቱት ጀግናው አፄ ቎ዎድሮስ በጀኔራል ናፔር ዚተመራውን ዚእንግሊዝ ጩር በለስ ቀንቷ቞ው ድል ባያደርጉትም መቅደላ ላይ በ1860 ዓ.እ ‘’እምተቀንዮ በነገደ ያፊት ፥ ይሄሰኒ መዊት” ብለው ራሳ቞ውን ሰውተዋል። አዎ ‘ዚአቢሲንያው አምበሳ በአሮፓ ድመት ተዋርጀ እጅ ሰጥ቞ ኚምገዛስ ዹማይቀሹውን ሞት ብመርጥ ይሻለኛል’ ብለው ፥ በፈሚንጆቜ አቆጣጠር April 13, 1868 (በእኛ በ1860 ዓ.ም)፣ ሊሚዳ቞ው ዚሚገባው ዹወገን ኃይልም ለጠላት አሳልፎ ስለሠጣ቞ው፣ ዚራሳ቞ውን ሺጉጥ ጥይት ጠጥተው፥ ኢትዮጵያን አንድ ለማድሚግ ኹ13 ዓመት ዚውስጥ ውጣ ውሚድ በኋላ ይህን በሚመስል አሳዛኝ ሁኔታ ተሰውተዋል።

ኹአፄ ቎ዎድሮስ አሳዛኝ እሚፍት በኋል ለሁለት ዓመት ያህል ንጉሥ ተክለ ጊዮርጊስ በሚል ዚዘውድ ስም ዚነገሡት ዋግሹም ጎበዜን ድል አድርገው ዚነገሡት አፄ ዮሐንስ 4ኛ እና ዹጩር መሪያ቞ው ዚነብሩት ጀግናው ራስ አሉላ አባ ነጋ ዚመሩት ዚኢትዮጵያ ጩር ፥ በ1867 ዓ.እ ጉንደት ላይ እና በ1868 ዓ.እ ጉራ ላይ ዚግብጜን ጩር ፣ በ1879 ዓ.እ  ዶጋሌ ላይ ዚኢጣልያንን ጩር ተዋግቶ ድል ተቃዳጅቶ ነበር። ኚዚያም በመቀጠል አፄ ዮሐንስ ጎንደርን ወሮ ዹነበሹውን ዚድርቡሜ/ሱዳን ጩር ለመዋጋት ዹሰሜኑን ግንባር ትተው ወደ ጎንደር ተመለሱ። ጎንደርን ነፃ ካወጡ በኋላ መተማ ኚሀገራ቞ው ድንበር ላይ መጋቢት 1 ቀን 1881 ዓ.ም ፥ በፈሚንጆቜ March 10, 1889 ለሀገራ቞ው ተሰውተዋል።

ስለዚህ እነዚህ ያለምንም ፋታ ኹውጭ ወራሪ ኃይል ጋር ለ20 ዓመታት ዹተደሹጉ ጊርነቶቜ ይህን ዛሬ ዚምናስበውን ዚአድዋን ድል በአፄ ምንይልክ ለተመራው ኅብሚ-ብሔራዊ ጩር ትልቅ ልምድና ወታደራዊ ተመክሮ ሠጥተውት ነበር። በአንፃሩ ደግሞ ለ20 ዓመታት ዹተደሹገው ዚማጥቃትና ዹመኹላኹል ጊርነት ብዙ ብሔራዊ ዚሀብት ምንጭ አስጚርሶ ነበር። ዹዘመነ መሳፍንት ስሜትም በአንድ አንድ አካባቢ ጚርሶ አልጠፋም ነበር። ኹዚህም በተጚማሪ ኹፍተኛ ድርቅ ሀገሪቷን ጎድቷት ስለነበር  ኚአድዋ ድል በኋላ ጣልያንን ኚኀርትራም ጭምር ጚርሶ ለማስወጣት ዹነበሹውን ወታደራዊ እቅድ እንዲደናቀፍ አድርጎታል። ስለዚህ ሰው ሠራሜና ዚተፈጥሮ ቜግሮቜ ተባብሚው ዚኢትዮጵያን ሕዝብ አጎሳቁለውት ስለነበር ነበራዊ ሁኔታው ለኢጣልያ ወራሪ ጩር ምቹ ሁኒታን ዹፈጠሹ መስሎ ይታይ ነበር። ሆኖም ግን ይህን ዚተፈጥሮና ሰው ሠራሺ ቜግር አፄ ምንይልክ በጣም አዋቂና አስተዋይ መሪ ስለነበሩ ሁሉንም በብልሀትና በትግስት ይዘውት ነበር። ባለቀታ቞ው እ቎ጌ ጣይቱ ብጡል ኃይለ ማርያምም ‘’መልካም ሚስት ለባልዋ ዘውድ ናት” እንደተባሉት ፥ እውነትም ዘውዳ቞ው ስለነበሩ ዹሚሠጧቾውን ምክር ሁሉ ንጉሠ ነገሥቱ በጥሞና ያዳምጡ ነበር። እ቎ጌ ጣይቱ በሀገራቜን ሥርዓተ ትምህት መሠሚት ኚውዳሎ ማርያም ጥሬ ንባብም አልፈው ዜማውን ፀ እንዲሁም ጟመ ድጓና ቁም ጜፈት ጭምር ደበሹ ታቊር ኢዚሱስ እዚተማሩ ያደጉ ሎት ነበሩ። ኹዚህም ሌላ ዚስሜኑ መስፍን ዚደጃዝማቜ ዉቀ ኃይለ ማርያም ወንድም ዚደጃዝማቜ ብጡል ኃይለ ማርያም ልጅ ስለነበሩ ዚቀገምድርንና ስሜንን ፥ ኚዚያም አልፈው ጠቅላላ ዹሰሜን ኢትዮጵያን ሕዝብ ስነልቊና በሚገባ ጠንቅቀው ያውቁ ስለነበር አፄ ምንይልክ “እ቎ጌ ጣይቱ ብርሃን ዘኢትዮጵያ “ ዹሚል ማኅተመ ስም ሠጥተዋ቞ው ነበር። እ቎ጌ ጣይቱ ጎንደሬ ብቻም ሳይሆኑ ኹወሎ ኊሚሞወቜና ሺሬ ኚትግራይዮቜም ተወላጅ ስለነብሩ ፥ ያኔ ዚጣልያን ጠቅላይ ምንስ቎ር ዹነበሹው ፍራንሲስኮና መሚብ ምላሺን “ኀርትራ” በሚል ስም በጣልያን ፓርላማ አሰይሞ ፥ ኹአፄ ዮሐንስ ዘመነ ዕሚፍት ጀምሮ ሲገዛ ዹነበሹው ጀኔራል ባርትዚሪ ውስጥ ውስቱን ዹሰሜን ኢትዮጵያን መሳፍንቶቜ በምንይልክ ላይ እንዲያምፁ ሲያደርጉት ዹነበሹውን ማባበል እ቎ጌቱ በነበራ቞ው ዚሥጋ ዝምድና ትስስር አክሜፈውታል። ማለት ዹሰሜን ኢትዮጵያ መሳፍንቶቜ ዚጠላትን ዚማባበልና ዹመኹፋፈል  ሎራ ሳይቀበሉት ቀርተዋል።

ጣልያን ኢትዮጵያን ጠቅልሎ ዚመግዛት ዓላማው ዚማይሳኚለት መሆኑን ኚተሚዳ በኋላ ዚኀርትራ ግዛቱ ብቻ በኢትዮጵያ በኩል እውቅና እንዲያገኝለት ወሰነ። አፄ ምንይልክም ዙርያውን በአውሮፓ ቅኝ ገዥ ኃይሎቜ ተኹበው ስለነብሩ ሁሉን ኚማጣት ብለው፥ ኹነበሹው ተጚባጭ ሁኔታ ተነስተን ስናዚው ሃሳቡን መቀበል ግድ እንደሆነባ቞ው መገመት አያዳግትም። ስለዚህ በሁኔታው አስገዳጅነት ሚያዝያ 25 ቀን 1881 ዓ.ም ኢጣልያ ዚኀርትራ ቅኝ ገዥ መሆኗን ዚሚያሚጋግጥ 19 አንቀጜ ያለው ስምምነት ወሎ ውስጥ ልዩ ስሙ ውጫሌ ኚተባለ ቀበሌ ላይ ተደሚገ። በተለይ አንቀጜ 17 በጣልያንኛ ዚተጻፈው ኹዐማርኛው ጋር ዹተቃሹነና አሻሚ ትርጉም ይዞ ነበር ለአውሮፓ መንግሥታትና ሕዝቊቜ ዚተበተነው። ኢትዮጵያ ዚኢጣልያ ጥገኛ (protectorate)እንደሆነቜና ኹውጭ መንግሥታት ጋር ዚሚኖራት ዚዲፕሎማቲክ ግንኙነት በኢጣልያ በኩል ካልሆነ እንደ ነፃ ሀገር በራሷ ብቻ ማድሚግ እንደማትቜል ተደርጎ ነው ለአውሮፓ መንግሥታት ዹተበተነው ።

ይህ ውል ዹተጭበሹበሹ እንደነበር በኢትዮጵያ በኩል ሊታወቅ ዚቻለውም አለቃ አጜመ ጊዮርጊስ ዚተባሉ ኢትዮጵያዊ ዹቋንቋ ሊቅ በጣልያንኛ ዚተጻፈውን እንዲመሚምሩት ተሠጥቷ቞ው ስለነብር ፣ አለቃ ይህን ነገር በሚገባ ለንጉሡ አደገኛነቱን አስሚዷ቞ው። ይህን እንደተሚዱ አፄ ምንይልክ ወደቀተ መንግሥታ቞ው እዚተመላለሰ ፀ ‘’ጌታዚና ግርማዊ’’ እያለ በለሰለሰ አንደበቱ በውዳሎ ኚንቱ ሲደልላ቞ው ዹነበሹውን ስኞር ኮንቲ አንቶሊኒ ዚተባለውን፥ ማለት ጣልያንን ወክሎ ውሉን ዹፈሹመውን ዲፕሎማት አስጠርተው ፥ አንቀጜ 17 ዹተጭበሹበሹና ኹዐማርኛው ቅጅ/ኮፒ በፍፁም ዹማይገናኝ መሆኑን እንደደሚሱበት ነገሩት። እሱ ግን በተለመደው ለስላሳ አንደብቱ ‘’ይህን ያለወት ሰው በመንግሥትዎ ላይ ቅን አስተሳሰብ ዹሌለውና በጠላትነት ሊነሳብዎ ያሰበ ሰው መሆን አለበት አንጅ ነገሩ ምንም ዹተጭበሹበሹ ትርጉም ዹለውም” ብሎ ለጊዜው አሳመና቞ው። ንጉሡም በአለቃ ላይ ተበሳጭተው አለቃን እንዲታሰሩ አደሚጓ቞ው። ‘እውነትና ብርሃን እያደር ይጠራል ‘ ነውና ፥ ሳይውል ሳያድር ሙሮ ማሪ ዎሎሜኩል ዚተባለ ፈሚንሳዊ ዲፕሎማት በጅቡቲ በኩል ወደ አንኮበር መጥቶ ልክ አለቃ አጜመ ጊዮርጊስ ዚተናገሩትን ነገር ሳይጚምርና ሳይቀንስ በማስሚዳት አገራ቞ው ኢትዮጵያ ዚጣልያን ጥገኛ አገር እንደሆነቜ ዚአንቀጜ 17ቱ ውል እንደሚያስሚዳ በአውሮፓ መንግሥታት ዘንድ ግንዛቀ እንደተጚበጠ ነገራ቞ው። ንጉሡም አለቃን ይቅርታ ጠይቀው ፈቷ቞ው።

አፄ ምንይልክ ይህን ኚተሚዱ በኋላ ለአውሮፓ መንግሥታት ማስተባበያ቞ውን ላኩ። ኢትዮጵያ ያቀሚበቜውን ማስተባበያ ያኔ ሊስተኛውን ዓለም በአብዛኛው በቅኝ ስትገዛ ዚነበሚቜው ታላቋ ብርታንያ  አልቀበለውም አለቜ። አፄ ምንይልክም እናንተ ባትቀበሉት ‘ኢትዮጵያ እጆቿን ወደ እግዚአብሔርና ልጆቿ ትዘሚጋለቜ’ ብለው በአምላካ቞ውና በሕዝባ቞ው ተማምነው አሻፈሚኝ አሉ። አንቀጜ 17ን ብቻም ሳይሆን ጠቅላላ ዚውጫሌን ውል ኢትዮጵያ ማፍሚሷን ወይም መሰሹዟን ንጉሠ ነገሥቱ ጥር 4 ቀን 1885 ዓ.ም. ለዓለም አሳወቁ። ፈሚንሣይና ሩሲያ ዚኢትዮጵያን ተቃውሞ በመቀበል ዚኢጣልያንን ዚኢትዮጵያ ዹበላይ ጠባቂነት እንደማይቀበሉት ተስማሙ። በተለይ ዚሩሲያው ንጉሥ ወይም ዛር ኒኮላስ ወታደራዊ እርዳታ ለማድሚግ ወሰኑ። ዹጩር መሣርያም በመላክ ውሳንያ቞ውን በድርጊት ፈጞሙ።

በዚህ ምክንያት ኚሁለት ዓመት ውዝግብ በኋላ ዚጣልያን ወራሪ ጩር መሚብን ተሻግሮ ደብሚ ሃይላ ላይ አደጋ ጥሎ አካባቢውን እንዲጠብቁ ተሹመው ዚነበሩትን ዚትግራይ ባላባቶቜ፣ ፊታውራሪ ንጉሀን፥ ቀኛዝማቜ ኃይለ ማርያምን፥ ቀኛዝማቜ አንድአርጋ቞ውንና ባላምባራስ በዹነን ወግቶ በመስኚሚም 29 ቀን 1888 ወሚራ መጀመሩን አፄ ምንይልክ ሰሙ። ኹዚህ በኋላ አፄ ምንይልክ ጥቅምት 2 ቀን 1888 ዓ.ም ዹሚኹተለውን ዚጊርነት አዋጅ አውጀው ኚአዲስ አበባ ወደ ሰሜን ጩር ግምባር ኚእ቎ጌ ጣይቱ ጋር ኅብሚ ብሔር ሠራዊታ቞ውን መርተው ለመንቀሳቀስ ተዘጋጁ። ዚጊርነቱ አዋጅ በዛን ጊዜው ዐማርኛ ይህን ይመስል ነበር።

ቃለ አዋጅ !

“እግዚአብሔር በ቞ርነቱ እስካሁን ጠላት አጥፍቶ፣ አገሬን ጠብቆ አኖሚኝ። እኔም እስካሁን በእግዚአብሔር ቞ርነት ገዛሁ። እንግዲህ ብሞትም ሞት ዹሁሉም ነውና ስለኔ ሞት ኣላዝንም። ደግሞም እግዚአብሔር አሳፍሮኝ አያውቅም። እንግዲህም ያሳፍሚኛል ብዚ አልጠራጠርም።

አሁንም አገር ዚሚያጠፋ፥ ሃይማኖት ዚሚለውጥ ጠላት እግዚአብሔር ዹወሰነልንን ባህር አልፎ መጥቷል። እኔም ያገሬን ኚብት ማለቅ ዹሰውንም መድኚም አይቾ እስካሁን ዝም ብለው ደግሞ እያለፈ እንደ ፍልፈል መሬት ይቆፍር ጀመር።

አሁን ግን በእግዚአብሔር ሚዳትነት አገሬን አሳልፌ አልሰጠውም። ያገሬ ሰው ! ካሁን ቀደም ዚበደልኩህ አይመስለኝም። በድዚህም ኹሆነ ለሀገርህ ስትል ይቅር በለኝ። አንተም እስካሁን አላስቀዚምኚኝም። ስለዚህ ጉልበት ያለህ በጉልበትህ እርዳኝ። ጉልበት ዹሌለህ ለሚስትህ፥ ለሃይማኖትህ፥ ለሀገርህና ለታሪክህ ስትል በጞሎትህ እርዳኝ። ወስልተህ ዹቀሹህ ግን ኋላ ትጠላኝ አለህ ፣ አልተውህም ! ማርያምን ! ለዚህ አማላጅ ዹለኝም ! “ ዹሚል ነበር ዹአዋጁ ቃል ።

አዋጁን አውጀው ወደ ሰሜን ጩር ግምባር ኚመሄዳ቞ው በፊት ዹተቀሹውንም ዚሀገሪቱን ክፍል ዙሪያውን አውሮፓውያን ኚበውት ስለነበር ወሰን ጠባቂ ጩር መመደብ ነበሚባ቞ው። በዚህ መሠሚት ዹጅማው ሹም ጅማ አባ ጅፋር ፥ ዹሊቃው ሹም ደጃዝማቜ ገ/እግዚአብሔርና ደጃዝማቜ ጆ቎፥ ዚወላይታው ሹም ንጉሥ ጩና ካዎና ሌሎቜ፥ ዚምዕራቡንና ደቡቡን ድንበር እንዲጠብቁ። በምሥራቅና በሰሜን ምሥራቅ ደግሞ ኹአፋር አርበኞቜ ጋር ተባብሚው በአሰብ በኩል ጠላት እንዳይመጣ እንዲጠብቁ ራስ ወልደ ጊዮርጊስ፥ ደጃዝማቜ ተሰማ ናደውና ዹወሂን አዛዥ ወልደ ጻድቃን 15,000 ጩር ይዘው እንዲሰለፉ ሁኖ ነበር።ዚመናገሻ ኹተማዋንና አካባቢውንም ራስ ዳርጌ ሣህለ ሥላሎ፥ ራስ ልዑል ሰገድና ደጃዝማቜ ኃይለ ማርያም 8000 ጩር ይዘው እንዲጠብቁ ተመድበው ነበር።

ይህን ካጠናቀቁ በኋላ ዹሰሜኑ ዘመቻ ቀጠለ። ዚመጀመሪያውን ዚጠላት ጩር አምባ ላጌ ላይ በፊታውራሪ ገበዹሁና ፊታውራሪ ተክሌ ዚተመራው ዚግንባር አብሪ ጩር በሻለቃ ቶዘሊን ይመራ ዹነበሹውን ዚጠላት ጩር  ኅዳር 28 ቀን 1888 ዓ.ም ደምስሰው ጠላት ሲጠቀምባ቞ው ዚነበሩትን መድፎቜና ሌላ መሳርያ ኚነብዙ ጥይቱ ማርኚው፥ ዚኢትዮጵያን ሠንደቅ ዓላማ ኚአምባይቱ ላይ ሰቅለው እያውለበለቡ ቆዩ። (ዚአምባላጌ ኚፍታ 11,279 ፊት ነው።) ቀጥለውም ግፋ ወደፊት በማለት ታህሣስ 29 ዚክርስቶስ ዚሥጋዌ ልደት መታሰቢያ ቀን መቀሌ ደርሰው መሺጎ ኹነበሹው ኚጠላት ጩር ጋር ፍልሚያ ጀመሩ። ነገር ግን ምሺጉን ሰብሮ መግባት ኹወገን በኩል ኹፍተኛ መስዋዕትነት ዹሚጠይቅ መሆኑ ስለተሚጋገጠ ፥ እ቎ጌ ጣይቱ ሲመሯ቞ው ኚነበሩት መካኚል 300 አርበኞቜን ጠላት ባልጠበቀው መንገድ ልኹው ፥ ጠላት ሲጠቀምበት ዹነበሹውን ዹውሀ ምንጭ ኣስደፈኑት። ኹ15 ቀን ቆይታ በኋላ ዚጠላትን ጩር በተለመደው ኢትዮጵያዊ ሰብአዊ ርህራሄ ምሺጉን ለቆ እንዲሞሺ ምህሚት አደሚጉለት። ዹዚህ ታሪክ ምንጭ አንዱ ኚሆኑት ኚአቶ ዮሐንስ መሞሻ ጜሑፍ ላይ ዹመቀሌውን ድል አስመልክቶ ዚገጠሙት ግጥም እንዲህ ይላል።

መቀሌ እንዳ ኢዚሱስ ጩር ያሰፈሚው ፥

አንድ ሺህ አንድ መቶው እውሀ እንዲጠማው፥

ምንጩን አዘግታ ጣይቱ አቃጥላው፥

ማጆር ጋሊያኖ ጉሮሮው ደርቆበት እንባ ሲወርደው፥

መኮነን አማልዶት እምዚ ምንይልክ በምህሚት ላኹው ።

ዚኢትዮጵያ ጩር በዚህ ሁኔታ ጠላትን ኹመቀሌ ካስለቀቀ በኋላ በቀጥታ ጠላት ሠፍሮበት ወደነበሹው ሕዳጋ ሐሙስና አዲግራት መሄዱን ትቶ በምዕራብ በኩል ወደ አድዋ ሄደ። ምክንያቱም ሕዳጋ ሐሙስና አዲግራት ላይ ዚጠላትን ምሺግ በቀላሉ መስበር እንደማይቻል ዹወገን ጩር መሹጃ ነበሚው። ዚጠላት ጩርም ዹወገን ጩር ወደ አዲግራትና ሕዳጋ ሐሙስ እንደማይመጣ ኚተሚዳ በኋላ ፥ ወደ ምዕራብ ተንቀሳቅሶ ኚአድዋ 30 ኪሎ ሜትር ርቀት ኚምትገኘው ሳውርያ ላይ ምሺግ ቆፍሮ 20,170 ዚታጠቀ ጩር ይዞ ዚኢትዮጵያ ጩር ጥቃቱን እንዲጀምር ይጠባበቅ ነበር። ነገር ግን ኢትዮጵያውያን በራሳ቞ው ወታደራዊ እቅድ እንጅ በጠላት ፕላን መሄድን ስላልፈለጉ ጥቃቱ ኚጠላት በኩል ዚሚጀመርበትን ዘዮ ማቀነባበር ጀመሩ። ማን እንደሚጀምር ሲጠባብቁ ግን በሁሉም በኩል ስንቅ እያለቀ ነው። ዚባሰው ግን በጣላት በኩል ነበር። በዚህም ምክንያት ጠላት ጥቃቱን እንዲጀምር ሁኒታዎቹ እያስገደዱት መጡና ዚአድዋው ትያትር /ትርኢት እንደሚኚተለው ሆነ።

ዚካቲት 20 ቀን 1888 ወደማታ አካባቢ ዹግፈኛውን ዚጣልያ ወራሪ ጩር ሲመሩ ዚነበሩት 5ቱ ጀኔራሎቜ እንትጮ ተራራ ላይ ድንኳና቞ው ወስጥ ተሰብስበው ዚጥፋት ተልዕኳ቞ውን ማሳካት ዚሚቜል ወታደራዊ ፕላናቾውን መቀዚስ ጀመሩ። ዚጀኔራሎቹም ስም ዹሚኹተለው ነበር። ዚኀርትራ ገዥ ዹነበሹው ጀኔራል አሚስቲ ባራትዚሪና አራቱ ዚብርጌድ ኣዝዊቜ ፥ ጀኔራል አልበርቶን፥ ጀኔራል አርሞንዲ፥ ጀኔራል ዳቊርሚዳ፥ እና ጀኔራል ኢለና ነበሩ። በብዙ ሺሕ ዹሚቆጠር ጣልያናዊና ጥቁር እራስ አስካሪ በዚያ ዘመን ደሹጃ እጅግ ዘመናዊ ሥልጠና በተሠጣ቞ው ዚበታቜ ዹጩር መኮንንኖቜ ስር ተሰልፎ ትእዛዝ ኹበላይ አዛዊቹ በመጠባበቅ በተጠንቀቅ ላይ ነበር። ያን ዹመሰለ ሠራዊት በአፍሪካ አህጉር ውስጥ ለውጊያ ሲሰለፍ በታሪክ ዚመጀመሪያው እንደነበር ብዙ ዚታሪክ ጠበብቶቜ ይስማማሉ።

20 ኪሎ ሜትር ራቅ ብሎ አድዋ ላይ ደግሞ ፣ ቀደም ብሎ ጣልያኖቜን በድንበር ሲኚላኚላ቞ው ዹነበሹው ዚራስ መንገሻ ዮሐንስ ጩር ብቻ ሳይሆን ባጠቃላይ ኹላይ ተደጋግሞ እንደተገለጠው ዹመላው ኢትዮጵያ ኅብሚ ብሔር ጩር በታላቁ ንጉሠ ነግሥት ምንይልክ ኃይለ መለኮትና በጀግናዋ እ቎ጌ ጣይቱ ብጡል ኃይለ ማርያም ዹበላይ አዛዥነት፣ በእግዚአብሔር ዹበላይ ጠባቂነትና በርሱም ፍፁም ታማኝነት፣ ሠራዊቱ ኹዚህ እንደሚኚተለው በሀገር ወዳድ አዛዊቜ ስር እዚጣለ ለመውደቅ በቆራጥነት ተሰለፈ።

በሰሜን በኩል ዚትግራይ ጩር በራስ መንገሻ ዮሐንስ አዛዥነት፣ በስተደቡብ በሜሎዳ ተራራ በኩል ያኔ ዹማህል ሰፋሪ እዚተባለ ዚሚታወቀውን ሠራዊት በመምራት ፊታውራሪ ገበዚሁ፣ ዹሐሹርን ጩር በመምራት ዹአፄ ኃይለ ሥላሎ አባት ራስ መኮነን ወ/ሚካኀል፣ ዚታቜ ወሎን ጩር በመምራት ንጉሥ ሚካኀል አሊ ፣ ዋግሹም ጓንጉል ፥ ደጃዝማቜ ኃይሉና (ዚራስ ካሣ አባት) ጃንጥራር አስፋው (ዚእ቎ጌ መነን አባት)ዹዋግን ፥ ዚላስታንና ዚአምባሰልን ጩር በመምራት በአድዋ ኹተማ ደቡብ በኩል ፣ ራስ መንገሻ አትኚም ዚኀፍራታን ፣ ራስ ወሌ ብጡል (ዹቮጌ ጣይቱ ወንድም) ዚቀገምድርንና ስሜንን ጩር በመምራት ፣ ደጃዝማቜ ባሻህና ሊቀ መኳስ አባተ ዚሜዋን ጩር በመምራት ፣ ንጉሥ ተክለ ሃይማኖት ዹጎጃምን ጩር በመምራት ፣ ደጃዝማቜ ባልቻ አባ ነብሶ ጀግናውን ዚኊሮሞና ዚጉራጌን ፈሹሰኛ ጩር በማሰለፍ ‘’ኢትዮጵያ ወይም ሞት !” እያሉ ለእናት አገራ቞ው ነፃነት እዚጣሉ ለመውደቅ ተሰለፉ።

ዚግብጹ ተወላጅ ብፁዕ አቡነ ማ቎ዎስ፥ ዚኢትዮጵያ ኊርቶዶክስ ተዋህዶ ቀተ ክርስቲያን ሀገሹ ስብኚት ሊቀ ጳጳስ ፥ ታቊተ ጜዮንን በማስያዝ ፣ ዚአኩስሙ ንቡሚ ዕድና ዚደብሚ ሊባኖሱ እጬጌ አፍሮ አይገባውን መስቀል ተሞክመው፣ኚአኩስም ቆይታ቞ው አድዋ ላይ ለውጊያ ወደተሰለፈው ብሔራዊ ጩር ሲጓዙ በተመለኚታ቞ው ጊዜ ሠራዊቱ “ዹሙሮ ጜላት/ ዹአማላክ እናት መጣቜልን” በማለት ዹበለጠ መንፈሳዊ ሞራልና ኢትዮጵያዊ ወኔ ተሰማው። በአምላኩ ኃይል ግፈኛውን ወራሪ ዚጣልያን ሠራዊት እንደሚያ቞ንፍ ያለምንም ጥርጥር እምነቱን በማሚጋገጥ ‘ግፋ ወደፊት ማለት ጀመሚ። ሊቀ ጳጳሱም “ ልጆቾ ሆይ ! በዛሬዋ ዕለት ፥ ዚካቲት 23 ፥ 1888፥ እግዚአብሔር አምላክ ኚእኛ ኚደካማዎቹ ጎን ተሰልፎ በግፈኛ ወራሪዎቜ ላይ እውነተኛ ፍርዱን ዚምናይበት ቀን ይሆናል። ዚቅዱሳን አባቶቻቜሁ ፥ ዚነቅዱስ ያሬድ፥ ዚነቅዱስ ላሊበላ፥ ዚነቅዱስ ተክለ ሃይማኖት፥ ዚነአባ ኀዎስጣ቎ዎስ ኹፋሌ ባህር፥ ዚነአባ ፊልጶስ ዘደብሚ ቢዘን፥ ዚነአባ ሳሙኀል ዘዋልድባ አምላክ ኚእናንተ ኹግፉአኑ ጋር ነው ! ሂዱ ወደፊት! ኊርቶዶክሳዊት ሃይማኖታቜሁን፥ መካነ ቅዱሳንና ሀገሹ እግዚአብሔር ዚሆነቜውን ቅድስት ኢትዮጵያንና ንጉሣቜሁን ተኹላኹሉ ! ኃጢአታቜሁ ይሰሚይላቜሁ።” በማለት ጾሎተ ንስሐ ለንጉሡና ለሠራዊቱ ሠጡ። ካህናቱም ኹዚህ ድርጊት ጋር ዚሚዛመደውን፥ ንጉሠ እስራኀል ዳዊት ኹ1,000 ዓመት ኚክርስቶስ ልደት በፊት ዹተነበዹውን ትንቢት በዚህ ታሪካዊ አካባቢ ዹተወለደው ኢትዮጵያዊው ቅዱስ ያሬድ በ520 ዓ.ም አካባቢ በደሹሰው ዹዜማ ስልት

  • ወወሀብኮሙ ትእምርተ ለእለ ይፈርሁኹ ፥ ኹመ ያምስጡ እምገጞ ቀስት፥ ወይድኀኑ ፍቁራኒኚ።
  • ጾርሁ ጻዳቃን ወእግዚአብሔር ሰምዖሙ ፥ ወእምኩሉ ምንዳቀሆሙ ያድኅኖሙ፥ ቅሩብ እግዚአብሔር ለዹዋሃነ ልብ ።
  • ይገንዩ ቅድሜሁ ኢትዮጵያ ፥ ወጞላእቱሂ ሀመደ ይቀምሁ።
  • አንተ ቀጥቀጥኮ አርስቲሁ ለኚይሲ ፥ ወወሐብኮሙ ሲሳዮሙ ለሕዝበ ኢትዮጵያ።
  • ኢትዮጵያ ታበጜህ እደዊሃ ሃበ እግዚአብሔር ፥ ነገሥተ ምድር ሰብህዎ ለአምላክነ ፥ ወዘምሩ ለስሙ እያሉ ይጞልዩ ነበር።

ዚእስልምና እምነት ተኚታይ ዚነበሩ ኢትዮጵያውያንም ኚክርስትና እምነት ተኚታይ ኢትዮጵያውያን ወንድሞቻ቞ውና እህቶቻ቞ው ተሰልፈው እኩል መስዋእትነት ኚፍለዋል። እንደ ካህናቱም ሁሉ መንፈሳውያን ሞኜወቹም ድዋ በመያዝ ወይም በመጾለይ አገራ቞ው ኢትዮጵያን ባህር አቋርጩ ኚመጣው ግፈኛ ጠላት ኚተቃጣባት ጥፋት እንዲታደጋት አምላካ቞ው አላህን በመማጾን ላይ ነበሩ። ክርስቲያኑም ሆነ ሞስሊሙ ዚክተት አዋጁ ኚታወጀበት ኚጥቅምት 2 ቀን 1888 ዓ.ም ጀምሮ ቀንና ሌሊት ዚጋራ አምላኩን ኹመማጾን አላቋሹጠም ነበር።

ዚጊርነቱ ዝግጅት ሰው ሰራሺ በሆነው ዘዮም ፥ ማለት በመሹጃ አሰባሰብም በኩል ዚተጫወተው ወሳኝ ሚና ነበሚው። ታሪኩ እንደዚህ ነበር። አውአሎም ሐሚጎት ዚተባለ ዚአካባቢው ተወላጅ ወጣት ለኢጣልያ መንግሥት በመሹጃ አቅራቢነት እንዲያገለግል ተቀጥሮ ይሠራ ነበር። ታድያ አውአሎም ምንም ቢሆን አፉ እንጅ ልቡ ወደወገኖቹ ያደላ ነበርና ፣ ጠላት በእናት አገሩና በወገኖቹ ላይ ሊፈጜመው ለተዘጋጀው ጥፋት ተባባሪ መሆንን አልመሚጠም። ይህም ኢትዮጵያዊ ንቃተ ህሊናው ኚጠላት ዹተማሹውን ዹመሹጃ አሰባሰብ ዘዮ አገሩንና ወገኑን እንዲጠቅምበት አስገደደው። ይህን ዹተቀደሰ ዓላማ ለጓደኛው ለብላታ ገ/እግዚአብሔር ያለምንም ፍርሀት ገለጞለት። ሁለቱ ጓደኞቜ ይህን ሲያሰላስሉ በነበሚበት ወቅት ውዝግቡ በሰላም እንዲፈታ ድርድር ቀጥሎ ነበር። ዹነዚህ ሁለት ኢትዮጵያውያን አለቃ ዹነበሹው ጣልያናዊው ዹመሹጃ መኮንን ስለድርድሩ  “ ኃያሉ ዚጣልያን መንግሥት ሠራዊት ይህን ዚኢትዮጵያን ዚዝንብ መንጋ ባንድ ቀን አራግፎ ግዛቷን መቆጣጠር ያቅተዋል ተብሎ ነው ድርድር እዚተባለ ጊዜያቜን ዹምናጠፋው ?” እያለ ሲደነፋ ለሀገራ቞ው ሕዝብ ያለውን ንቀት ሲገልጜ፥ አውአሎም እዚሰማ ውስጡ ይቃጠላል። ኚዚያ ብላታ ገ/እግዚአብሔር አውአሎምን ኚራስ መንገሻ ዮሐንስ ጋር ዚሚተዋወቅበትን መንገድ ይፈልግና ኚራስ ጋር አገናኘው። ራስ መንገሻም ዹአውአሎምን ታማኝነት ካሚጋገጡ በኋላ ዹሚኹተለውን ዘዮ ይቀይሳሉ።

ዘዮውም ይህ ነበር። ዚካቲት 21 ቀን ማርያም ስለሆነቜ አብዛኛው መሳፍንት ኚሚመራው ጩር ጋር ቀተ ክርስቲያን ለመሳለምና ለመጾለይ ወደ አኩስም ጜዮን እንደሚሄድ፣ ዚንግሥቲቱ ወንድም ራስ ወሌም ስለሞቱ ንጉሡና ንግሥቲቱ በኀዘን ላይ እንደሆኑ፣ አንዳንድ መሳፍንቶቜም ዚሚመሩትን ጩር ይዘው ጣልያንን ድል ማድሚግ እንደማይቻል ተስፋ ቆርጠው እዚኚዱ ወደዚመጡበት እዚተመለሱ እንደሆነ ፣ ዹተቀሹው ሠራዊትም ስንቅ ጚርሶ ምግብ ፍለጋ ተኹዜን ተሻግሮ ጠለምትና ወልቃይት ድሚስ እንደሄደና ንጉሡና ንግሥቲቱ ኚጥቂት ዚክብር ዘበኞቻ቞ው ጋር ድንኳና቞ው ውስጥ ስለሚገኙ፥ ስንቅ ፍለጋ ወደ ጠለምትና ወልቃይት ዚሄደውና፥ ወደ ኣኩስም ጜዮን ዹሄደው ሠራዊት ኚመመለሱ በፊት እሑድ ዚካቲት 23 ቀን አደጋ ቢጣል በቀላሉ ድል አድርጎ ንጉሡንና ንግሥቲቱን መማሹክ እንድሚቻል አድርጎ፥ አዘናጊና ዚተሳሳተ መሹጃ አውአሎም ለጀኔራል ባራትዚሪ እንዲሠጠው ይሆናል። እ቎ጌ ጣይቱ እጅግ በጣም አርቆ አሳቢና ጥበበኛ ስለነበሩ ፥ ዹጠበቀ እምነት እግዚአብሔርም ስለነበራ቞ው፥  ኹአውአሎም ጋር ዹተቀዹሰውን ዘዮ በቃል ኪዳን ለማጠንኹር አውአሎምን እንደልጃ቞ው እጁን ጚብጠው እዚሳቡ ወደ ድንኳና቞ው ይዘውት ገቡ። “ ይህን ዚማቀርብልህን ምግብ እንደ ክርስቶስ ሥጋ ወደሙ ቆጥሚህ እናት አገርህንና ወገንህን ላትኚዳ በመሃላ ቃል ገብተህ ይህን ያቀርበኩልህን ምግብ ተመገብልኝ “ አሉት። እርሱም “ አገሬንና ወገኔን ለጠላት አሳልፌ ብሠጥ ፥ ሰማይና ምድርን ዹፈጠር አምላክ ይፍሚድብኝ” በማለት ይህን ጠንኹር ያለ ዹተለመደውን አስተማማኝ ኢትዮጵያዊ ቃል ኪዳን ኚገባ በኋላ ምግቡን ተመግቩ ፥ ኢትዮጵያ በድል አድራጊነት ዚተወጣቜበትን ወሳኝ ብሔራዊ ግዳጁን ለመወጣት ወደጠላት ጩር ሠፈር ጉዞውን ቀጠለ።

ኚጠላት ካምፕ እንደ ደሹሰ ኹላይ ዹተዘሹዘሹውን ዚተሳሳተ፥ ግን ለጠላት እጅግ አስደሳቜ ዚሚመስለውን መሹጃ ለጀኔራል ባራትዚሪ አቀሚበ። ባራትዚሪም በቀሚበለት መሹጃ ሚክቶና ተደስቶ ኚምሺጉ ወጥቶ ምንይልክን ለመማሹክና አገሪቱንም በቅኝ ለመግዛት እዚተዝናና መጣ። ዹተናቀው ዚኢትዮጵያ ጀግና ሠራዊት ግን ቀደም እንደተገለጞው በዚምሺጉ ሁኖ ማህል እስኚሚገባ ድሚስ አድፍጊ ጠበቀው። ኚዚያማ ያን ነጭ ዚሮማ ስንዎ በጋለ ጥቁር ምጣድ ይቆላው ጀመር !! (እልልልልል!!)። በዚሁ ዕለት ፥ እሑድ ዚካቲት 23 ቀን 1888 ዓ.ም. ወደ 11 ሰዓት አካባቢ እንደ አንድ አገር ሕዝብ በአንድ አመራር ሥር ዹተሰለፈው ዚኢትዮጵያ ጀግና ሕዝብ፥ በአምላኩ በእግዚአብሔር ሚዳትነት ፥ በጀግና መሪዎቹ አርቆ አሳቢነትና አገር ወዳድነት ጠላቱን ደምስሶ ብሔራዊና ሰብአዊ ማንነቱን ጠብቆ አስጠበቀ። በዚህም ታሪካዊ ድል ኚጠላት እብሪተኛ ጀኔራሎቜ መካኚል ጀኔራል አርሞንዲና ጀኔራል ዳቊርሚዳ ሲገደሉ ፣ ጀኔራል ኢለና ወደኀርትራ እንደአጋጣሚ ኹተወሰነ ጩር ጋር አመለጠ። 262 ዚኢጣልያን ተወላጅ መኮንኖቜና 4,000 ተራ ወታደሮቜ ሲገደሉ ፥ 954 ዚደሚሱበት ሳይታወቅ ቀርቷል (Missing in action)። 470 ነጭና 958 ጥቁር ራስ ባንዳዎቜ ቆስለዋል። ጀኔራል አልቚርቶን ጚምሮ 1,900 ነጭና ኹ1,000 በላይ ወደውም ሆነ ተገደው ኚጠላት ጋር ተሰልፈው ወገኖቻ቞ውን ዹወጉ ዚመሚብ ምላሺ አበሟቜ ተማርኚዋል። 56 መድፎቜና 11,000 በዘመኑ ዚነበሩት ቀላልና ኚባድ መሳሪያዎቜ ሊገመት ካልተቻለ ጥይት ጋር ተማርኳል። ክ100,000 በላይ ዹሚሆነው ዚኢትዮጵያ ሠራዊት ይዟቾው ዹተሰለፈው 40 መድፎቜና 80,000 ዹሚሆኑ ቀላል ዹጩር መሣሪያዎቜ እንደነበሩ ሪቻርድ ፓንክሚስትና ሌሎቜ ዚታሪክ ጞሓፊዎቜ ዘግበዋል። ኹወገን በኩልም ለሀገራ቞ው ክብርና ነፃነት መስዋዕት ዚሆኑት ጥቂቶቜ አልነበሩም። ኹ5,000 በላይ ተሰውተዋል። 8,000 ቆስለዋል። ኚተሰውት ውስጥ ዹአፄ ምንይልክ ዚአኚስት ልጅ፥ ዹወ/ሮ አያህሉሜ ሣኅለ ሥላሎ ልጅ ደጃዝማቜ ባሻህና ፊታውራሪ ገበዹሁ ይገኙበታል።

ይህን በመሰለ ሁኔታ ለመጀመሪያ ጊዜ አውሮፓዊ ዹሆነ ዹነጭ ኃይል በጥቁር አፍሪካዊ ኃይል በመደምሰሱ ድሉ ዚኢትዮጵያውያን ብቻም ሳይሆን በዚያ ዘመን ተንቆና ተዋርዶ በቅኝ ግዛትና በባርነት ቀምበር ሥር ሲማቅቅ ለነበሹው ዹመላው ጥቁር ዘር ሁሉ ነበር ተደርጎ ዚታዚው። አዎ በአፍሪካ ፥ በካሚብያንና በሰሜን አሜሪካ በዘሹኛ ነጮቜ መንግሥትና ሕዝብ ሰብአዊነታ቞ው ተርሰቶ ዚነበሩት ጥቁሮቜ ዚደስታ ጭላንጭል ዚሰሙበት ዕለት ነበር። ኹዚህም ዕለት ጀመሮ ነበር እነዚህ ህዝቊቜ ለነፃነታ቞ው ቆርጠው ለመታገል ዹበለጠ ዚተበራቱት። ወርሐ ዚካቲትንም ልዩ ትኩሚት ሠጥተው ‘’Black History Month/ ታሪካዊ ዚጥቁሮቜ ወር “ እያሉ እስኚዛሬ ድሚስ በዚዓመቱ እንዲያስቡት ካደሚጋ቞ው አንደኛው ምክንያት ይህ ዚአድዋ ድል ነው።

እንግዲህ ኚተለያዩ ዚታሪክ ምንጮቜ ዚቀዳዋ቞ው ፥ አባቶቻቜንና እናቶቻቜን ዚሠሩት እውነተኛው ትውልድ አኩሪ ታሪክ ኹሹጅሙ በአጭሩ ይህን ይመስላል። ጥያቄው ግን ዛሬስ ያቜ ዚታሪክና ዚብሔሚሰቊቜ ቀተ መዘክር ዚሆነቜው አገራቜን ኢትዮጵያ ዹ 1888ቱ አይነት ጠንካራ ዹውጭ ወራሪ ክብሚ ወሰኗን ጥሶ ቢገባ ለድል ዚሚያበቃት አስተዋይ መሪ አላት ወይ ? ዚጋራ ማንነቱ መገለጫ ኹሆነው ኚኢትዮጵያዊነቱ ይልቅ ለዹግል ማንነቱ፥ ማለት ለዐምሐራነቱ፥ ለኊሮሞነቱ፥ ለትግሬነቱ፥ ለጉራጌነቱ፥ ለአፋርነቱ፥ ለወላይታነቱ፥ ለአገውነቱ ወዘተርፈ..ቅድሚያ እንዲሠጥ ተደርጎ እዚተተካ ያለው አዲሱ ትውልድ ፣ ነገ ኹነገ ወዲያ አንድነቱን ጠብቆ፥  ዚሚመጣበትን ዹውጭ ጥቃት ሊመክት  ይቜላል ማለት እንዎት ይቻላል? ይህ ዹአሁኑ ትውልድ ለብሔር ማንነቱ ነው እንጅ ቅድመ ሁኔታ መሥጠት እንደማይቜል እዚተነገሚው ያለው ኢትዮጵያዊነቱን እኮ በሕገ መንግሥቱ ኣንቀጜ 39 ላይ በግልጜ እንደተቀመጠው እስኚፈለገው ድሚስ ነው። ማለት ዚብሔር ማንነት ግዎታ ሲሆን ኢትዮጵያዊ ማንነት ግን በአማራጭ ደሹጃ ነው ትውልዱ እንዲቀበለው ተደርጎ እዚተተካ ያለው። ለዚህ እኮ ነው ብሔራዊ ማንነት ኚብሔር ማንነት ይቅደም ዹሚል አጀንዳ ያላ቞ው በግልም ሆነ በድርጅት ደሹጃ እንዲዳኚሙ ሁነው በግል ማንነት ላይ ያተኮሚ አጀንዳ ያላ቞ው እዚተጠናኚሩ ዚመጡት።

ታድያ ዚዛሬ 119 ዓመት ‘’ አባት ያበጀው ለልጅ ይበጀው ‘’ ብለው ኚአራቱም ማዕዘናት በአንድ ኢትዮጵያዊ ማንነት፥ በአንድ ሠንደቅ ዓላማ አርማ፥ በአንድ መንግሥታዊ አመራር ሥር፥ አንድ አገር አንድ ሕዝብ ብለው ተሰልፈው ደማቾውን ቀለም አጥንታ቞ውን ብዕር አድርገው ያስመዘገቡትን አኩሪ ታሪክ ጠብቀን ለተተኪው ትውልድ ማስተላለፍ አይጠበቅብንም? ለጥያቄው መልሱ አወንታዊ ነው መሆን ያለበት። አዎ እኛም ዛሬ ለነገው ትውልድ ዚሚያኮራና ዹነገው ትውልድ ዛሬ እኛ አባቶቻን ዚሠሩትን አኩሪ ታሪክ እያሰብነው እንዳለነው ሁሉ  ነገም እኛን እንድንታወስ ዚሚያደርግ ጥሩ ታሪክ እዚሠራን እንለፍ። ይህ ነው ዹሰውን ልጅ ኚእንስሳት ልዩ ዚሚያደርገው። እናም እንሰባሰብ እንጅ አንበታተን። አንድነት ኃይል መሆኑን ይህ አድዋ ላይ ኹ 119 ዓመት በፊት ዚተሠራው ታሪክ ዘለዓለማዊ ዹሆነ ታላቅና ቋሚ ምሥክር ነውና በእኩልነት ላይ ዚተገነባ አንድነት እንገንባ እያልኩ ዝግጅቮን ኹዚህ ላይ አጠናቃለሁ። በጥሞና ስላዳመጣቜሁኝ አመሰግናለሁፀ እግዚአብሔር ይሥጥልኝ።

 

ኹበደ አገኘሁ ቊጋለ፣ ዚካቲት 23 ቀን 2007 ።

 

መወድስ ቅኔ ዘአለቃ ዘወልዮ ዘአንኮበር ለአፄ ምንይልክ ዚተሠጠ።

ትውልድ ዹኀልፍ ወሰነ አበው ወትውልድ ይተርፍ እምነ አቡሁ በግብር ፀ

ምሳሌ ዝኒ ላዕሌኹ ሣህለ ማርያም (ምንይልክ)ደብርፀ

ሐሰውኹሂ ኢትበለኒ እሙነ ዜናሁ ለሰሎሞን በኩርፀ

ጠይቅ ወተዘኹር ፥ እመ ነባቢሁ ተቀብሚ አምጣነ ንባቡ ኢይትቀበርፀ

በይነ ጜድቅሂ ወበይነ ርትዕ ወበይነ ዚዋሃት መንክር ፀ

እስኚነ ትግሬ ይመርሐኹ ስብሐተ ዹማንኹ ፍዳ ጞርፀ

አርቲዐኚሂ ፍኖተ ማዕኹለ ወሎ ሀገር ፀ

ተሠራሕ ለኮንኖ ወንገሥ በጎንደር።

The post ዹ 119ኛው ዝክሹ አድዋ ፀ 1888   – ኹበደ አገኘሁ ቩጋለ appeared first on Zehabesha Amharic.

↧

ዚአድዋ ድል በዓል በሚኒሶታ ተኹበሹ

$
0
0

ESM 2

ecm minnesota

(ዘ-ሐበሻ) ዚኢትዮጵያ ማህበሚሰብ (ኮምዩኒቲ) በሚኒሶታ ያዘጋጀው 119ኛው ዚአድዋ ድል በዓል በሚኒሶታ ተኚብሮ ዋለ::

በሚኒሶታ ኚኢትዮጵያ ኮምዩኒቲ ኚወጣትም ሆነ ኚአዛውንቶቜ ዚተውጣጡ ዚተለያዩ ዚማህበሚሰቡ ክፍሎቜ በተገኙበት በዚሁ በዓል ላይ ዚአድዋ ድል በዓል በተለይ ለኢትዮጵያውያን እና ለጥቁር ሕዝቊቜ ያለው ትልቅ ም ዕራፍ ተዘክሯል::

ዛሬ በተኹበሹው በዓል ላይ በክብር እንግድነት ዚተገኙትና ስለአድዋ ድል ገለጻ ዚሰጡት ዶ/ር ዳንኀል ሲሆን ዚአድዋ ድል ኚጥቁር ሕዝቊቜ ታሪክ ጋር ያለውን ተያያዥነት አውስተው ዚተለያዩ ገለጻዎቜን ሰጥጠዋል::

በዚሁ ዕለት በስፍራው ዹተገኙ ዚማህበሚሰቡ አባላት እንዲሁ በበዓሉ ዙሪያ ትምህርታዊ አስተያዚቶቜን እንደሰጡም በስፍራው ዹተገኘው ዚዘሐበሻ ዘጋቢ አስታውቋል::

The post ዚአድዋ ድል በዓል በሚኒሶታ ተኹበሹ appeared first on Zehabesha Amharic.

↧
Viewing all 15006 articles
Browse latest View live