Quantcast
Channel: Ethiopian News | ዘ-ሐበሻ | Latest News Provider | News For All
Viewing all 15006 articles
Browse latest View live

“ሶማሊያ የሚገኙ የጦር ሠራዊት አባላት ሲበደሉ ያመናል”–አርበኞች ግንቦት 7

$
0
0

ethiopian militery ethiopian militery1

የተባበሩት መንግሥታት ማኅበር የሚሰጠው ገንዘብ ህሊናቸውን በሰወራቸው፤ የህወሓት አባላት በሆኑ ጄኔራሎች አዝማችነት ሶማሊያ የገባው ኢትዮጵያዊ ድሃ ወታደር እጣ ፈንታ በጣም አሳዛኝ ደረጃ ላይ ደርሷል። በየእለቱ ኢትዮጵያዊያን ወታደሮች እየተገደሉ፤ አስከሬናቸው በጎዳናዎች እየተጎተተና እየተቃጠለ ነው። ሶማሊያ የሚገኙ የኢትዮጵያ ሠራዊት አባላት ወገኖቻችን ናቸውና በእነርሱ ላይ የሚደርሰው ስቃይ ይሰማናል፤ ሲበደሉ ያመናል፤ ጭንቀታቸው ይጨንቀናል። ወገኖቻችን ናቸውና የደህንነታቸው ጉዳይ ያገባናል።

የህወሓት ጄኔራሎች ሙሉ ትኩረታቸው ያለው በእያንዳንዱ ወታደር ስም ከተባበሩት መንግሥታት በሚያገኙት ገንዘብ መጠን ላይ ነው። ለሶስት ሣምንታት ብለው የገቡበት ጦርነት እነሆ አስር ዓመታት አስቆጥሯል። አንዱ የገቢያቸው ምንጭ ነውና ጦርነቱ ለሌላ አስር ዓመታት ቢራዘም ለእነሱ ደስታቸው ነው። ኢትዮጵያዊው ምስኪን ወታደር ግን አዛዦቹ እንዲያልቅ በማይፈልጉት ጦርነት ውስጥ ገብቶ መስዋዕትነት ይከፍላል፤ ሲወድቅ የሚያነሳው የለም፤ መስዋዕት ሲሆን የክብር አሸናኘት የለውም፤ ቤተሰቦቹም ይኑር ይሙት አያውቁም። ይህ ሁላችንንም ሊያስቆጣ የሚገባ ግፍ ነው።

ኢትዮጵያን ለመታደግ ብሎ የዘመተን ወታደር ስለኢትዮጵያ ግድ በማይሰጣቸው፤ ጥቅማቸውን ብቻ በማሳደድ ላይ ያሉ አዛዦች ቸልተኝነት ምክንያት ለስቃይ፣ ሰቆቃና ውርደት መዳረግ የለበትም። በሶማሊያ በሚገኙ የኢትዮጵያ ወታደሮች ላይ የሚደርሰው በደል በሁላችም ላይ የደረሰ በደል ነው፤ በእነርሱ ስብዕና ላይ እየደረሰ ያለው ውርደት በአገራችን ላይ የደረሰ ውርደት ነው።

የጦሩ አዛዦቹ በወታደሩ ስቃይና ሞት ከብረው የከተማ ድሆችን እያፈናቀሉ ሕንፃዎችን እየገነቡ፤ የባንኩን፣ የኢንሹራንሱን፣ የገቢና ወጪ ንግዱን እያጧጧፉ ነው። የወታደር ልብስ ቢለብሱም፤ “ጄኔራል እከሌ” ተብለው ቢጠሩም በተግባር መጥፎ ነጋዴዎች እንጂ ወታደሮች አይደሉም። እነዚህ የስም ጄኔራሎች በጦርነት ውስጥም የሚታያቸው ንግድና ገበያ ነው። በእንደነዚህ ዓይነቶች አዛዦች ተመርቶ ጦርነትን ማሸነፍ አይቻልም።

አርበኞች ግንቦት 7 የአንድነትና ዲሞክራሲ ንቅናቄ፣ በህወሓት የጦር አዛዦች ብቃት ማነስ፣ ስግብግብነትና ቸልተኝነት ሳቢያ በሶማሊያ እየሞቱ፣ እየቆሰሉ፣ አስከሬናቸው እየተዋረደ ስላለው ኢትዮጵታዊያን የሚሰማውን ጥልቅ ሀዘን ይገልፃል።
ከሶማሊያ ውጭም የኢትዮጵያ ወታደር የሚገኝበት ሁኔታ እጅግ አሳዛኝ ነው። በተለይም በሀገር ውስጥ የኢትዮጵያ ወታደር እንደ ስሙ “የአገር መከላከያ ሠራዊት” በመሆን ፋንታ ወገንን ማጥቂያ ሠራዊት እየሆነ ነው፤ አገርን በመከላከል ፋንታ ወገንን ማጥቃት የሠራዊቱ የዕለት ተዕለት ተግባር ሆኗል። ለዚህ አሳፋሪ ተግባር ሠራዊቱ ራሱ መላ ሊፈልግለት ይገባል።

አርበኞች ግንቦት 7 እየታገለ ያለው ሠራዊቱን ከሚገኝበት ከዚህ አሳፋሪ ሁኔታ ለማውጣትም ጭምር ነው። ሠራዊቱ የአዛዦቹ መገልገያ መሣሪያ መሆኑ ማብቃት አለበት። ሠራዊቱ ወገንን ማጥቂያ መሆኑ ማክተም አለበት። ሠራዊቱ ወደ ውጭ አገራት ለግዳጅ ሲላክ ተገቢውን ክብር ሊሰጠው፤ ጥቅማ ጥቅሞቹም ሳይሸራረፉ ሊያገኝ ይገባል። የሠራዊቱ አባላት እየደኸዩ፣ ቤተሰቦቻቸው እየተራቡና እየታረዙ አዛዦቹ በሀብት ላይ ሀብት የሚያጋብሱበት ሁኔታ ማብቃት አለበት። ይህ አዋራጅ የሠራዊት አያያዝ መቀየር አለበት፤ መቀየር ደግሞ ይቻላል።

እያንዳንዱ የሠራዊት አባል በግል የጠራ ፀረ-ህወሓት አገዛዝ አቋም ይያዝ፤ ከሚመስሉት ወዳጆቹ ጋር ውስጥ ውስጡን ይምከር፤ አርበኞች ግንቦት 7 ጋር የምስጢር ግኑኝነት ለመመስረት ይጣር፤ ጦሩ ውስጥ እያለ ሥርዓቱን የሚዳክሙ ተግባራትን ይፈጽም። ህወሓትን ለማዳከም የሚደረግ ጥረት ትንሹም ትልቅ ዋጋ አለው። ሠራዊቱ የህወሓት መገልገያ አለመሆኑ ማስመስከሪያ ወቅት አሁን ነው። የህወሓት አምባገነን አገዛዝን ከውስጥም ከውጭም ሆነን እንፋለመዋለን፤ እንደምናሸንፍ ጥርጥር የለውም።

ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!!!

The post “ሶማሊያ የሚገኙ የጦር ሠራዊት አባላት ሲበደሉ ያመናል” – አርበኞች ግንቦት 7 appeared first on Zehabesha Amharic.


ፍስሐ ደስታ፤ የቀድሞው የኢትዮጵያ ም/ፕሬዚደንት፤ ስለ አዲሱ መጽሃፋቸው “አብዮቱና ትዝታዬ” ይናገራሉ

$
0
0

(SBS Amharic Radio) “የኢሕአፓን ቆራጥነት፣ የመኢሶንን ርዕዮተዓለማዊ ብስለትና የደርግን ብሔራዊ የአገር ፍቅር ስሜት አንድ ላይ ማድረግ ብንችል ኖሮ ኢትዮጵያ ለታላቅ ደረጃ በደረሰች ነበር።”
– ፍስሐ ደስታ

ፍስሐ ደስታ፤ የቀድሞው የኢትዮጵያ ምክትል ፕሬዚደንት፤ ስለ አዲሱ መጽሃፋቸው “አብዮቱና ትዝታዬ” ይናገራሉ

The post ፍስሐ ደስታ፤ የቀድሞው የኢትዮጵያ ም/ፕሬዚደንት፤ ስለ አዲሱ መጽሃፋቸው “አብዮቱና ትዝታዬ” ይናገራሉ appeared first on Zehabesha Amharic.

[የማለዳ ወግ …ለመስጠት ፣ የተሰጣችሁ ኑ…] 2.4 ሚሊዮኑን ካሳ ለምን አንቀበልም አሉ ?

$
0
0

FB_IMG_1445555267317

blatena
የብላቴናው መሀመድን ቤተሰቦች እንርዳ !
… ጋኑን በጠጠር እንደግፍ !
==========================

* የመሀመድ ቤተሰቦች 2.4 ሚሊዮን ሪያል ካሳውን ለምን አንቀበልም አሉ ?
* ለመሀመድ ቤተሰቦች ድጋፍና እርዳታውስ ለምን አስፈለገ ?
* የመርጃ መንገድ አማራጮች ምን ምን ናቸው …

2.4 ሚሊዮኑን ካሳ ለምን አንቀበልም አሉ ?
===========================
ብላቴናው መሀመድ ዛሬ እንደ ጓደኞቹ እየቦረቀ እንዳይማር በሀኪሞች ስህተት የአልጋ ቁራኛ ሆኗል ። መሀመድ አልጋ ላይ ሆኖ ላይሰማና ላያይ ያሰናከሉት ሀኪሞችና ሀኪም ቤቱ ለፍርድ ይቀርቡ ዘንድ አድካሚ ጉዞን ዘጠኝ አመት ለዘለለ ጊዜ ተጉዘዋል።

የመሀመድ ቤተሰቦች አበባቸውን የመነጠቅ ያህል እገረ ተከሉ መልከ መልካም ድንቡሽ የ4 ዓመት እድሜው ብላቴና መሀመድ ድክ… ድክ ብሎ ለቀላል ህክምና ገብቶ ተሰናክሎባቸዋል ፣ አባትና እናት ብሎም ቤተሰብና ዘመድ አዝማድ ቅስማቸው ተሰብሯል ። እንዲህ ሆኖ ዘጠኝ አልፎ ፣ አስረኛ አመት ተጠግቷል !

ከምንም በላይ በእስልምና የኢማን መሰረት በሆነው ( ቀዳ ወል ቀድር ) ” በፈጣሪ ዘንድ ቀድሞ በተጻፈው የሰው ህይዎት የሚያምኑት የብላቴናው መሀመድ ቤተሰቦች በልጃቸው የሆነው የፈጣሪ ፈቃድ መሆኑን አጥብቀው ያምናሉ ፣ ፈጣሪ አላማረሩትም ። በሆነው ሁሉ ፈጣሪን “ተመስገን!” እያሉ ለልጃቸው መሰናከል ያለ እውቀታቸው በሰሩት ቀዶ ጥገና ጥፋት የፈጸሙትን ሀኪሞችና ሆስፒታሉ በልጃቸው የሰሩት ስህተት ፍርድ ያገኙ ዘንድ ገና ከጅምሩ ተግተዋል። ለብላቴናው መሰናከል ምክንያት የሆኑ ወንጀለኞች ናቸው ብለው በማመን ወደ ፍርድ ቀርበው ቅጣታቸውንና የጉዳት ካሳ ማግኘት ሀቅ በቅዱስ ቁርአን ሳይቀር የተረጋገጠ የተፈቀደ ነውና ይህ መብታቸው እንዲከበር ስለፍትህ አቤት በማለት ላይ ይገኛሉ!

አድጋካሚው የፍትህ ጥያቄ ላለፉት 9 ዓመታት ተሸፋፍኖ ቢባጅም በደል ተዳፍኖ የማያስቀረው ፈጣሪ ረድቷቸው የመጀመሪያ ደረጃ ፍትህ ብስራትን ከወራት በፊት አግኝተዋል ! ብላቴናው መሀመድ የሚገኝበት የዶር ሱሌማን ፈቆ ሆስፒታል ዶክተሮች በተሰራ የህክምና ስህተት መፈጸሙን የሳውዲ ጤና ጥበቃ ሚኒስቴር የዶክተሮች ቡድን አረጋግጧል። ቡድኑ ምንም እንኳን በኮሚቴ ተዋቅሮ ስድስት አመታት ጉዳዩን በማጥናትና በመመርመር ሀኪሞች አስቀርቦ የጥፋተኝነት ውሳኔ ባያሳልፍም ሀኪም ቤቱን ጥፋተኛ ያደረገበት ሰነድም ይፋ ሆኗል። በውሳኔው ሆስፒታሉ ብላቴናው መሀመድን በቀጣይ መደገፍ እንደ አስፈላጊነቱ በነጻ ህክምና የመስጠት ኃላፊነትና 2.4 ሚሊዮን ሪያል ካሳ እንዲሰጥ የስምምነት ውሳኔ ተላልፏል። ዳሩ ግን በረባ ባልረባ ሰበብ ለተበዳይ ህክምና አጓድሎ ለአመታት የተበዳይን ቤተሰቦች ጉዳዩን ሰልችተው እንዲተውት ለማሰላቸት ሲሰራ የከረመው ሆስፒታል አስተዳደር ውሳኔ እንደተሰጠ አስታማሚ የብላቴናው መሀመድን እናት ከሰጧት መጠለያ በኃይል በማስወጣት ” 2.4 ሚሊዮን ሪያል ካሳ የምከፍለው ወላጆቹ በህክምና መሳሪያ የሚንቀሳቀሰውን ታዳጊ ስታስወጡ ነው!” በማለቱ በቤተሰቡ ዘንድ ተቀባይነት አላገኘም ። ይህን የማይቀበሉት እናቱና ቤተሰቦች አይደሉም ። ኩሩና ሰበአዊዋ እናት ሀሊማ ” ልጀን በገንዘብ አልለውጥም ፣ ልጀን ወደ ነበረበት መልሱልኝ! ” ብላ በምሬት የተናገረችበትን ዝርዝር ዘገባ በታዋቂ ጋዜጦች በሳውዲ ጋዜጥና በአረብ ኒውስ የተከታተሉ የህክምና ባለሙያ ” ገንዘብሽን ተቀብለሽ ልጅሽንም ውሰጅ! ” የተባለችበትን እርምጃ ሲቃወሙ በሰጡት አስተያየት እንዲህ ብለዋል ” As a medical worker myself, I feel sorry for the boy and his mother… We should be the one giving comfort to those who rely and trusted us… If the ministry has verdict that the hospital is at fault, then even if the mother receives the monetary compensation; the hospital should still give treatment to this boy even its forever! Taking the boy out of the life support machine is haram BUT if the boy is brain dead and arrested then he shouldnt be resuscitated. BUT to intentionally remove him from life support? No.. Please..” ” እንደ ህክምና ባለሙያ በልጁና በመሀመድ ላይ በተፈጠረው በጣም አዝናለሁ ፣ አምነውነው ወደ ህክምና ለሚመጡ ሰዎች ምቾትና ተገቢ ግልጋሎት እርዳታ የማድረግ ኃላፊነት ያለብን የህክምና ባለሙያዎቹ ነን …

የጤና ጥበቃ ሚኒስትር ሆስፒታሉ ጥፋተኛ ነው ብሎ ውሳኔ ካሳለፈ ሆስፒታሉ ለእናቱ የእናትነት ካሳ monetary compensation ከሰጠ በኋላ ልጆን እስከ መጨረሻ የማሳከም ኃላፊነት አለበት ። ልጁን ከህክምና መርጃ መሳሪያ ማላቀቅ ሀጢያት ነው ። ምናልባት አንጎሉ የማይሰራ ከሆነ እርዳታ ሊደረግለት ይገባል እንጅ ሆን ተብሎ ከህክምና መርጃ መሳሪያ ማላቀቅ ተገቢ አይደለም … ” በማለት ሙያዊ ምክራቸውን ሰጥተዋል !

የብላቴናው አባት በሚኖርበት የመካ ከተማ እየሰራ ቤተሰቡን ሲደግፍ ሚስት የመካ ቤቷንና ባሏን ርቃ ከቀረች ልጇ ከአሚና ጋር በመሆን ከልጇ ጎን ላለፉት አስርት አመታት አልተለየችም። እናት ሀሊማ ሙዘይን በሌለ ከወዲያ ወዲህ ብላ ያልነቃ የተኮላሸባት የስደት መከራ የዘር ፍሬዋን በስስት እያየች እያስታመመች ፣ ልጇን እያስተማረች የምትገፋው ህይዎት ከባድ ሆኗል ። ያም ሆኖ ከገንዘብ ይልቅ ሰብዕናን አስቀድማ በሆስፒታሉ ባሳለፈችው ህይዎት የተፈራረቀባት እንግልትና ያሳለፈቻቸው የስቃይ አመታት ታሪክ ተነግሮ አያልቅም ። በሀብትና ጸጋ ተማምኖ ፣ በማን አለብኝነት እብሪት የታበየውና የታዳጊውን የመሀመድን ብሩህ ህይዎት ያጨለመው ሀኪም ቤት ኃላፊዎች ካሳውን ከፍለው ለመሀመድ የተሻለ ህክምና መትጋት ሲገባቸው ይህን የማድረግ ፍላጎት አላሳዩም ። ይባስ ብለው የጥፋተኝነት ፍርዱ ሲሰጥ ከመሳሪያ እርዳታ ውጭ ላፍታ መንቀሳቀስ የማይችለውን ተገፊ እጓለ ማውታ እናቱ ” ይዛ ትዎጣ !” ማለቱ ሊሆን የማይችልና የከበደ በመሆኑ ፈጣሪዋ እንደማያጓድልባት የምትናገረው እናት ፍትህን ፍለጋ እጣ ነፍሷን መባዘኗ ማናችንም ለዘገየው ፍትህ እስኪሳካ ስትደክም ልንደግፋትና ስለ ሰብዕና ብለን ከጎኗ ልንሆን ግድ ብሏል … !

ድጋፍና እርዳታው ለምን አስፈለገ ?
======================
ድጋፍና እርዳታው ለምን አስፈለገ ? በሚለው ርዕስ ዙሪያ ማብራሪያ እንድሰጥበት ያስገደዱኝ ምክንያት አለ። ይህም ለብላቴናው መሀመድ ቤተሰቦች የመንግስት ተወካዮች ድጋፍ ይጎላል በሚል ላቀረብኩት ጭብጥ ያለው የመረጃ ግብአት ያመማቸው አደግዳጊ ጭፍን የመንግስት ተወካይ አጋፋሪዎች ቀጠን ያለች ዘመቻ ቢጤ መጀመራቸውን በመረዳቴ ድጋፍ ሰጭዎችን ግራ እንዳያጋቡብኝ ግልጽ ፍላጎቴን ለማሳዎቅ በመሻት ነው ። ከተቀነባበረው ስም ማጥፋት ጎን ለጎን እርዳታውን የመሰብሰብ ሀሳብ ሳቀርብ በእርዳታ ስም ሀብት ማከማቸት ፍላጎት እንዳለኝ በመግለጽ ገፍተውበታል ። ያም ሆኖ ይህ የተራ ወሮበላ አካሄዳቸው የጀመርኩትን እንደማያስቆመኝ ከመግለጽ በተጓዳኝ እርዳታው ያስፈለገበትን ምክንያት ለቀሪ ወዳጆቸ ማሳወቁን አስፈላጊ ሆኖ አግኝቸዋለሁ !

” የፍትህ ያለህ “በማለት እያነባች ፍትህ ርትዕ ጎድሎባቸው አስር አመት እተጠጋው አስቸጋሪ ውጣ ውረድ ስታልፍ ልጇን አሚናን ይዛ በመንከራተት ሲሆን በቤት ኪራይና በትራንስፖርት ህይቷ የተመሰቃቀለ ሆኗል። ላለፉት ዘጠኝ አመታት የመሀመድን ጉዳይ በመከታሉ በኩል አንዳች ድጋፍ ያላደረጉላት በሪያድ የኢትጵያ ኢንባሲ ኃላፊዎች የመሀመድን ቤተሰቦችን የፍትህ ጥያቄ ፍርድ ተሰጥቶት እንኳ በማስፈጸሙ ረገድም ሆነ ጉዳዩን ወደ ሳውዲ ባለስልጣናት በማድረስ እርባና ያለው ስራ ሰርተው አላየንም ። እርግጥ ነው የጅዳ ቆንሰል መ/ቤት ከዘጠኝ አመታት በኋላ ከሰድስት ወራት በፊት በመሀመድ ጉዳይ ጤና ጥበቃ ውሳኔ በሰጠበት ዋዜማ ጀመሮ ጉዳዩን መከታተል ቢጀምርም የሆስፒታሉን የጥፋተኝነት ውሰኔ ሰነድ በእጃቸው እያለ ጉዳዩ ከነበረበት ፈቀቅ የማድረግ አቅሙን አጥተውታል !

አጠቃላይ የመሀመድ ጉዳይ በዚህ መሰሉ ሂደት መገኘቱ ለሚቆረቁረን ዜጎች ቢያንስ በሁነኛ አዋቂ ባለመያዙ የጉዳዩ መጓተት ይታየናልና ያሳስበናል ። በዚህ መልኩ የጉዳዩ መጓተትም የልጇን መጨረሻ ለመከታተል የመካ ቤቷን አፍርሳ ጅዳ በቤት ኪራይና በትራንስፖርት ፈተና የገጠማትን እናት በአደባባይ እርዱኝ ብላ ባትናገረውም ክልትሟን ያየን እንረዳት ዘንድ ግድ ሆኗል ! ይህን ድጋፍ ለማድረግ ያቀተብኩትን ጥያቄ በቅን ልቦና ለተቀበላችሁ ወገኖቸ ያለኝን አክብሮት እየገለጽኩ ፣ እርዳታውን የመሰብሰብ ሀሳብ ሳቀርብ በእርዳታ ስም ሀብት ማከማቸት መላ መምታቴን በመጠቆም ለፍርድ እንደምቀርብ ላስጠነቀቃችሁ ስንኩሎች ልብ ይስጣችሁ በማለት የጀመርኩትን እርዳታ ማሰባሰብ እንደምገፋበት የማበስራችሁ በደስታ ነው !

እርዳታውን ለማሰባሰብ ያሉት አማራጮች…
===========================

1ኛ) በጅዳ የተለያዩ አካባቢዎች እርዳታ የሚሰበሰብባቸው ቦታዎች
> ሀየል ሰላማ > ሀየል በዋዲና ጀፋሊ
> ሀየል ሄራ > ሀየል ስካን
> ሀየል ድፋዕ አልመደኒ > ሀየል ረውዳ
> ሀየል ጃሚያ > ሀየል መኮሮና
> ሀየል ኢነኪሽ ሻረዕ ትግራይ

ከላይ ያልተጠቀሱ ቦታወችን ጨምሮ በተጠቀሱት የሀበሻ መገናኛነት በሚታወቁ የተለያዩ ድርጅቶች ሱቆች፣ ምግብ ቤቶች ፣ ሻሂ ቤቶችን ጨምሮ የእቃ መላኪያ ካርጎዎች ባላቸው ወገኖች በኩል እርዳታውን የማሰባሰብ እቅድ በዋናነት ይዣለሁ ። ለዚህ አማራጭ እቅድ መሳካታ ባለድርጅቶች ስልኮቻቸውን ያቀብሉን ዘንድ ትብብርን በዋናነት እጠይቃለሁ!

2 ኛ) ሌላው ከጅዳ ውጭ ባሉ ከተሞች አለያም በተላያዩ የአለም ክፍሎች የምትገኙና እርዳታ ማድረግ ፈቃደኛ የሆናችው ወገኖች እርዳታውን በዌስተር ዩኒየን በሚከተለው የእናት ሀሊማን አድራሻ መላክ ትችላላችሁ:

Name: HALIMA MUZEMIL – HASSEN
ID / Iqama no. 2187347097
Mobile: 00966 597938672
Jeddah, Saudi Arabia

3ኛ ) በተጠቀሰው አድራሻ መላክ የማትችሉ በተለይም ሳውዲ የምትገኙ የሳዋ አለያም የሞባይሌ ካርድ በመግዛት በመልዕክት ማስቀመጫ የሚስጥት ቁጥሩን በሞባይል ቁጥር 0597938672 በመላክ እርዳታ ማድረግ ይቻላል !

4ኛ) ከላይ በተጠቀሰው አድራሻ መላክ የማትችሉና በተለይም በስራ ቦታ ላይ ሆናችሁ በአካል እርዳታውን ማቀበል የምትፈልጉ በውስጥ መስመር አድራሻችሁን መላክና እርዳታ ማድረግ ትችላላችሁ !

* ለእርዳታ ድጋፉ ” የተሻለ አማራጭ አለ !” የምትሉ ከሆነም አሳውቁኝ ፣ ዋናው አላማ ግፉአኑን መደገፍ ነውና ከምክክሩ የሚገኘው ሁሉ ይበጀናል!

ወዳጆቸ ሆይ …
============
እንደተለመደው ይህንን የእርዳታ ጥሪ ላልሰማ አሰሙ አሰራጩት ፣ share አድርጉት !

አጋሮቸ ሆይ …
==========
ኑ የተገፉትን እንርዳ … አበው ” ጋን በጠጠር ይደገፋል ” እንዳሉት ለመስጠት ፣ የተሰጣችሁ ኑ “ጋኑን በጠጠር እንደግፍ !” …ለሚያልፍ ቀን የማያልፍ ስራ እንስራ ! ቢያንስ ” ነግ በኔ ነው ” ብለን እንተባበር ፣ እንደጋገፍ !
ብላቴናው መሀመድንና ቤተሰቡን ለመደገፍ አቅማችን ያልፈቀደ በጸሎት እንርዳቸው !

በጎነት ደግሞ ለራስ ነው ፣ ለነፍስ እርካታ !

ነቢዩ ሲራክ
ጥቅምት 12 ቀን 2008 ዓም

The post [የማለዳ ወግ … ለመስጠት ፣ የተሰጣችሁ ኑ…] 2.4 ሚሊዮኑን ካሳ ለምን አንቀበልም አሉ ? appeared first on Zehabesha Amharic.

(ሰበር ዜና) 300 መንገደኞችን ጭኖ ወደ አሜሪካ ሲበር የነበረው ድሪምላይነር የኢትዮጵያ አውሮፕላን አየር ላይ እንዳለ ሞተሩ መሥራት አቆመ

$
0
0

dream liner dream liner 3 dreamliber ethiopia dreamliner4
(ዘ-ሐበሻ) ንብረትነቱ የኢትዮጵያ አየር መንገድ የሆነውና ከአዲስ አበባ ተነስቶ በአየርላንድ በኩል ወደ አሜሪካ ሲበር የነበረው የበረራ ቁጥሩ ET-500 የሆነው 787-8 ድሪምላይነር የኢትዮጵያ አውሮፕላን አትላንቲክ ውቅያኖስ ላይ ችግር ስላጋጠመው ተመልሶ ወደ ደብሊን ለማረፍ መገደዱን ዘደይሊ ሜይል ጋዜጣ ዘገበ::

ዛሬ ከጠዋቱ 6:00 አካባቢ 300 የሚሆኑ መንገደኞችን ጭኖ ከአየር ላንድ ደብሊን አውሮፕላን የተነሳው ይኸው ድሪምላይነር አውሮፕላን ወደ ዋሽንግተን ዲሲ በረራ ላይ እንዳለ የአንደኛው አውሮፕላን ሞተር ሥራ በማቆሙ ተመልሶ ደብሊን ላይ እንዲያርፍ ተደርጓል:::

ለአንድ ሰዓታት ያህል በአየርላንድ ቆይታ አድርጎ ጋዝና ሌሎች ምግቦችን ለተሳፋሪዎች የጫነው ይኸው ቦይንግ 787-8 አውሮፕላንድ ለሁለት ሰዓት ተኩል ያህል ወደ ዋሽንግተን ዲሲ ጉዞ ለማድረግ በአየር ላይ መቆየቱን ዘ-ሐበሻ ከደይሊ ሜይል ያገኘችው መረጃ ያስረዳል:: የአውሮፕላኑ አንድ ክንፍ ሞተር ሥራ በማቆሙ የተነሳ ከ2:30 ዓየር ላይ ቆይታ በኋላ ወደ ደብሊን የተመለሰው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ድሪም ላይነር አውሮፕላንድ ከጠዋቱ 8:30 አካባቢ በሰላም ማረፉም ተዘግቧል::

ይህ አውሮፕላን ወደ ዋሽንግተን ዲሲ የማይበር ሲሆን የኢትዮጵያ አየር መንገድ ተቀያሪ አውሮፕላን ከፍራንክፈርት ጀርመን በመላክ የበረራ 500 ተጓዦች እንደገና በረራቸውን በ እንግሊዝ ሰዓት አቆጣተር 1 ሰዓት ላይ እንደሚጀመሩ ዘሐበሻ ያገኘችው መረጃ ይጠቁማል;:

ድሪምላይነር አውሮፕላኖች እንዲህ ያለው ችግር ሲያጋጥማቸው ይህ የመጀመሪያው አይደለም::

 

ከዚህ ቀደም:-

በ2013 ዓ.ም:- ድሪምላይነር ቦይንግ 787 ግዙፍ አውሮፕላን ገጠመው በተባለው የባትሪ ችግር ምክንያት ከመሬት እንዳይነሳ ለ3 ወራት ያህል በመላው ዓለም ቢታገድም የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግን ድሪም ላይነር አውሮፕላን ማብረሩ ይታወሳል::

አሁንም በዚያው በ2013 ዓ.ም ተሣፋሪ ባልነበረበት አይሮፕላን ላይ ዛሬ የተነሣ እሳት የለንደኑ ሂትሮው አይሮፕላን ማረፍያ እንዲዘጋ አድርጓል። እሳቱ የተነሳው ድሪምላይነር ቦይንግ 787 የኢትዮጵያ አየር መንገድ አይሮፕላን ውስጥ ነበር:: በአይሮፕላኑ ላይ ጢስ በታየበት ጊዜ ሞተሩ እየሠራ እንዳልነበረና ለስምንት ሰዓታት ያህል እዚያው ቆሞ እንደነበረ እንዲሁም ለምሽት በረራ የተዘጋጀ እንደነበረ የአጋጣሚው መንስዔ ምን እንደሆነ እንደማይታወቅ የአየር መንገዱ ሥራ አስፈጻሚ ገልጸው ነበር::

The post (ሰበር ዜና) 300 መንገደኞችን ጭኖ ወደ አሜሪካ ሲበር የነበረው ድሪምላይነር የኢትዮጵያ አውሮፕላን አየር ላይ እንዳለ ሞተሩ መሥራት አቆመ appeared first on Zehabesha Amharic.

“ተመስገንን ማየት አትችሉም!”

$
0
0

yetemesgen enat

ከታሪኩ ደሳለኝ

ወንድማችን ተመስገን ሀሳቡን በነጻነት ስለገለጸ እና ጽሁፎችን በጋዜጣ ስላተመ ብቻ ሶስት ዓመት ተፈርዶበት ወደ ዝዋይ እስር ቤት ከተላከ ዛሬ 374 ቀናት ሆነው፡፡ በተለያየ ጊዜ ተደጋጋሚ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች ቢደርስበትም ሁሉን ችሎ ዛሬ ላይ ደርሷል፡፡ ለሚያሰቃየው የወገብ እና የጆሮ ህመም ህክምና ሳያገኝ ዛሬም ህመሙን እየታገለ አለ፡፡ የታሰረበትን አንደኛ ዓመት በማስመልከት ይህንን ችግሩን እና የሚደርስበትን እንግልት አስመልከቶ እኛም፣ ወዳጆቹም ለመናገር ሞክረናል፡፡ አቤቱታችንን እና ጩኸታችንን ተከትሎ ችግሮቹ ይስተካከላሉ ብለን ብናስብም ይባስ ብሎ በገደብ የተፈቀደለት የቤተሰብ ጥየቃ እንዳያገኝ ከዚህ ሳምንት መጀመሪያ ጀምሮ ተከልክሏል፡፡

ወንደሞቹ ወደ ዝዋይ እስር ቤት ተመላልሰን ያጋጠመንን ከዚህ በታች አንብቡት እና እናንተው ፍረዱ፡፡ አንዴ አይደለም ሁለት፣ ሶስት፣ አራት ጊዜ “አይቻልም” ተብለናል፡፡

ክልከላ 1፡- እሁድ ጥቅምት 7/ 2008 ጠዋት ታላቅ ወንድማችን ዝዋይ ሰደርስ በአዋራና በፀሀይ ተቃጥሎ ነበር፡፡ የዝዋይ እስር ቤት መንገድን የቀመሰ ያውቀዋል፡፡ የእስር ቤቱ መግቢያ በር ላይ የተጠያቂ ስም ሲያስመዘግብ “ተመስገን ደሳለኝ” አለ፡፡
“እሱን መጠየቅ አይቻልም” አለ መዝጋቢው የእስር ቤት ወታደር፡፡
“ለምን?” ጠየቀ ወንድማችን፡፡
“ትላንት ማታ የደረስን ትዕዛዝ ነው”
“ማነው ያለው?”
“ከበላይ ነው”
“ምን ማለት ነው?”
“በማንም እንዳይጠየቅ ማለት ነው፡፡ አሁን ተመለስ” የእስር ቤቱ ወታደር ቆፍጠን ያለ ትዕዛዝ ሰጠ፡፡
“እሺ ምግቡን ላስገባ” ወንድማችን በመጨነቅ ጠየቀ፡፡
“አይቻልም” ቁርጥ ያለ ክልከላ፡፡

ክልከላ 2፡- ሰኞ ጥቅምት 8/2008
ሌላኛው ወንድማችን ወደ ዝዋይ እስር ቤቱ አቅንቶ “የተመስገን ወንድም ነኝ” ሲል ፈጣኝ ምላሽ ተሰጠው፡፡
“የያዝከውን ምግብ ይዘህ ቀኝ ኋላ ዙር” ከጠባቂዎቹ ወታደሮች አንዱ የሰጠው መልስ ነበር፡፡
“በምን ምክንያት?” ወንድማችን ጠየቀ፡፡
“አይመለከትህም!”
“ወንድሜ እኮ ነው!”
“እናውቃለን፡፡ ትዕዛዝ ነው!”
“እሺ ምግቡን እንኳን ላስገባ”
“አይቻልም፡፡ ውጣ!”

temesgen desalegn

ክልከላ እና ፍቃድ መሳይ 3፡- ማክሰኞ ጥቅምት 9/2008
ከአዲስ አበባ በጠዋት ተነስቼ ረፋድ ላይ ዝዋይ እስር ቤት ደረስኩ፡፡
“ተመስገን ጋር ነው የምገባው” አልኩኝ ለተረኛ መዝጋቢ ወታደር፡፡
“ምኑ ነህ?”
“ወንድሙ”
“ግባ” አላምንኩም!
የያዝኩትን ምግብ አስፈትሼ ከሩጫ በማይተናነስ እርምጃ ተመስገን ወደሚጠየቅበት ታዛ ፈጠንኩ፡፡ ለወታደሮቹ እንዲጠሩልኝ ስሙን ሰጥቼ ተቀመጥኩኝ፡፡ ተሜ ሳይመጣ 40 ደቂቃ አለፈ፡፡ አንድ ወታደር በብስክሌት መጥቶ “ተነስና ውጣ፡፡ በስህተት ነው የገባኸው” አለኝ፡፡
ከተሜ በሜትሮች ርቀት ያህል ርቀት ተቀምጩ ሳላየው መውጣቴ ቢያስጨንቀኝም እኔም እንደወንድሞቼ ከመጠየቅ ወደኋላ አላልኩም፡፡
“ማነው አይጠየቅም ያለው?”
“ትዕዛዝ ነው” ባለፉት ሁለት ቀናት ስንሰማው የነበረው ተመሳሳይ መልስ ተሰጠኝ፡፡
“እሺ የያዝኩትን ምግብ ላቀብለው”
“አትሰጠውም”
“እሺ ከኃላፊ ካለ አገናኘኝ” አልኩት ወታደሩን
ወታደሩ አጠገቡ ካለው ወታደር ጋር በአይኑ ተነጋግሮ በምልክት ቢሮውን አሳየኝ፡፡ የያዝኩትን ስንቅ አስቀምጩ “አስተዳዳር” የሚል ጽሁፍ በሩ ላይ ከተለጠፈበት ክፍል አንኳኩቼ ስገባ ሰባት በኃላፊነት ደረጃ ላይ እንዳሉ ማዕረጎቻቸው የሚያሳብቁ ወታደሮች ተሰባስበው አገኘኋቸው፡፡
የሰብሳቢ ወንበር ላይ ፈንጠር ብሎ የተቀመጠው ወታደር “ምንድነው?” አለኝ
“ወንድሜን አትጠይቅም ተብዬ ነው” መለስኩ፡፡
“ማነው ስሙ?”
“ተመስገን ደሳለኝ”
የተማከሩ በሚመስል ሁኔታ አንድ ላይ “እሱን መጠየቅ አይቻልም” አሉኝ፡፡
“ለምን?”
ሰብሳቢው ወታደር “አያገባህም” ብሎኝ አጠገቡ ያለውን መገናኛ ሬድዬ አንስቶ “የጋዜጠኛ ተመስገን ወንድም ነኝ ባይ እንዴት እዚህ ድረስ መጣ” ሲል ጠየቀ፡፡
የሬድዮን መልስ ልሰማ ስል “ውጣ እና በር ላይ ጠብቀኝ” አለ
ወጣሁ፡፡ እኔ ከወጣሁ ከ15 ደቂቃ በኋላ ሁለት ሬድዮ የያዙ ወታደሮች መጥተው ወደ መጠየቂያው ቦታ በድጋሚ ወሰዱኝ፡፡ ስደርስ ተሜ በስድስት ወታደሮች ተከቦ አገኘሁት፡፡ እኔን ካመጡኝ ወታደሮች ጋር ሲደመሩ ስምንት ሆኑ ማለት ነው፡፡ ከተሜ ጋር ሰላምታ ተለዋውጠን ማውራት ጀመርን፡፡
“ማዘር ምን ሆና ነው ያልመጣችሁት?” ጠየቀ ተሜ፡፡
“ኧረ! ምንም አልሆነችም፡፡ ከእሁድ ጀምሮ አትገቡም ብለውን ነው” አልኩት፡፡
ተሜ ወታደሮቹን እየተመለከተ “ለምንድነው የተከለከልኩት?” አለ፡፡
ሬድዮ የያዘው ወታደር ወደ እኔ እየተመለከተ “አሁን እሱን አናግረው” አለው፡፡
“ጉዳዩ ከእሱ ጋር አያይዝም” ተሜ መለሰ፡፡
ወታደሩ ወዲያውኑ “ተነስ” አለኝ
“ወዴት?” አልኩት
ተሜ ጣልቃ ገብቶ “ጉዳያችሁ ከእኔ ጋር መሰለኝ” አላቸው፡፡
መልስ አልመለሱትም፡፡ አንደኛው ወታደር ወደ እኔ ዞሮ “አንተ ሂድ” አለኝ፡፡
ሶስተ ደቂቃ በማይሞላ መተያየት ከሰላምታ የዘለለ ነገር እንኳ ሳናወራ ለመውጣት ተነሳሁ፡፡ የተሜን አይን አይን እያየሁ ሰወጣ ተሜ ስምንት ወታደሮች እንደከበቡት እያወራ ነበር፡፡ ምን እንደሚል መስማት አልቻልኩም፡፡ ከእስር ቤቱ ወጣሁ፡፡

ክልከላ 4፡- ሐሙስ ጥቅምት 11/ 2008
ሰኞ ዕለት ተሜን ሳያይ እንዲመለስ የተደረገው ወንድማችን ዝዋይ እስር ቤት ሲደርስ ገና ከበር “ተመስገንን መጠየቅ አይቻልም” አሉት፡፡
“ማክሰኞ ወንድሜ ገብቶ ነበር”
“አልገባም፡፡ ገብቶም ከሆነ በስህተት ነው”
የሚለው ሲያጣ “እሺ ያመጣሁትን ስንቅ ላቀብለው”
“አይቻልም ተመለስ”

ከሰኞ እስከ ሐሙስ በተደጋጋሚ ተሜን ለማየት እና ስንቅ ለማቀበል ያደረግነው ሙከራ እንግዲህ ይህን ይመስላል፡፡ “ይህ ተመስገናችሁ የእኛ እስረኛ ነው፡፡ እኛ ደግሞ ህክምና እንደከለከልነው፣ መርጠን በሰው እንዳስጠየቅነው፤ ዛሬ ደግሞ ማንም እንዳይጎበኘው ማድረግ መብታችን ነው፡፡ ስለዚህ ከዚህ በኋላ ማንም እሱን መጠየቅ አይችልም” ብለዋል የዝዋይ እስር ቤት ሹሞች፡፡

ተሜ ህገመንግስታዊ መብቱ ተገፍፎ፣ ሰብዓዊ መብቱ ተጥሶ እና በህመም እየተሰቃየ እስከመቼ ነው የሚቀጥለው?

The post “ተመስገንን ማየት አትችሉም!” appeared first on Zehabesha Amharic.

የቃሊቲ ማረሚያ ቤት “አንዳርጋቸው ጽጌ እኔ ጋር የሉም”አለ

$
0
0

• ‹‹የስርዓቱን ሽፍትነት ያመላክታል›› 3ኛ ተከሳሽ አቶ ደናሁን ቤዛ

• ‹‹የሚቀርብልን ምግብ ለእንሰሳትም መቅረብ የማይገባው ነው›› 2ኛ ተከሳሽ አቶ አሸናፊ አካሉ

በነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተር

በእነ ዘመነ ካሴ የክስ መዝገብ ከ2ኛ -5ኛ መዝገብ ለተከሰሱት አቶ አሸናፊ አካሉ (2ኛ ተከሳሽ)፣ አቶ ደናሁን ቤዛ (3ኛ ተከሳሽ)፣ አቶ ምንዳዬ ጥላሁን (4ኛ ተከሳሽ) እና አቶ አንሙት የኔዋስ (5ኛ ተከሳሽ) በመከላከያ ምስክርነት የተጠቀሱት አቶ አንዳርጋቸው ፅጌ ቃሊቲ ማረሚያ ቤት እንደሌሉ ማረሚያ ቤቱ ለፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 19ኛው ወንጀል ችሎት በላከው ደብዳቤ ገልፆአል፡፡ 19ኛ ወንጀል ችሎት ሀምሌ 29/2007 ዓ.ም የቃሊቲ ማረሚያ ቤት አቶ አንዳርጋቸውን ለምን እንዳላቀረበ እንዲያብራራ፣ እንዲሁም ለምስክርነት እንዲያቀርብ ለዛሬ ለጥቅምት 12/2008 ዓ.ም ለአራተኛ ጊዜ ቀጠሮ ሰጥቶ የነበር ቢሆንም ማረሚያ ቤቱ አቶ አንዳርጋቸው ቃሊቲ እንደሌሉ በደብዳቤ አሳውቋል፡፡

Andargachew Tsige

ተከሳሾቹ ማረሚያ ቤቱ ሲያጉላላቸው ቆይቶ አሁን የለም ማለቱ ትክክል እንዳልሆነ የገለፁ ሲሆን 2ኛ ተከሳሽ አቶ አሸናፊ አካሉ ማረሚያ ቤቱ ምላሽ የሰጠው በአራተኛው ትዕዛዝ መሆኑን ጠቅሶ የፍርድ ሂደታቸውን ከሚገባው በላይ እያጓተተ እንደሆነ ለፍርድ ቤቱ ገልፆአል፡፡ ‹‹መከላከል ከጀመርን አንድ አመት ከስድስት ወር ሆነ፡፡ በግዞት ነው ያለነው፡፡ የሚቀርብልን ምግብ ለእንሰሳትም መቅረብ የማይገባው ነው›› ያለው አቶ አሸናፊ የማረሚያ ቤቱን ምላሽ ‹‹ፌዝ ነው›› ብሎታል፡፡

3ኛ ተከሳሽ አቶ ደናሁን ቤዛ በበኩሉ አቶ አንዳርጋቸው ፅጌን በመከላከያ ምስክርነት ሲጠቅሱ አቃቤ ህግ አቶ አንዳርጋቸው ፅጌ የሞትና የእድሜ ልክ ፍርደኛ እንደሆኑ በመጠቆም ተቃውሞ አሰምቶ እንደነበር፣ የእድሜ ልክና የሞት ፍርደኛ ቃሊቲ እንደሚታሰር ገልፆ ማረሚያ ቤቱ አቶ አንዳርጋቸው እንደሌሉ መግለፁ ‹‹የስርዓቱን ሽፍትነት ያመላክታል›› ብሏል፡፡ ‹‹የእድሜ ልክ ወይንም የሞት ፍርደኛ የት ነው የሚታሰረው?›› ሲልም ፍርድ ቤቱን ጠይቋል፡፡
3ቱ ተከሳሾች የፀረ ሽብር ግብረ ኃይሉና ጠቅላይ ሚኒስትሩ አቶ አንዳርጋቸውን እንደያዙ በቴሊቪዥን መግለፃቸውን አስታውሰው አሁንም ለሁለቱ አካላት ደብዳቤ እንደሚፅፉ ለፍርድ ቤቱ አሳውቀው የነበር ቢሆንም ከ6ኛ-9ኛ ያሉት ተከሳሾች ማረሚያ ቤቱ በፈጠረው ችግር የአቶ አንዳርጋቸውን ምስክርነት ለመስማት የፍርድ ሂደታቸው እየተጓተተባቸው በመሆኑ የአቶ አንዳርጋቸው ምስክርነት ቀርቶ ብይን እንዲሰጣቸው ጠይቀዋል፡፡

ሆኖም ግን 4ኛ ተከሳሽ አቶ ምንዳዬ ጥላሁን ‹‹ከአንዳርጋቸው ጋር ተገናኝተህ መመሪያ ተቀብለሃል ስለተባልኩ አቶ አንዳርጋቸው መጥቶ መመስከር አለበት›› ሲል አሁንም አቶ አንዳርጋቸው እንዲቀርቡለት ጥያቄውን አቅርቧል፡፡ ፍርድ ቤቱም 4ኛ ተከሳሽ አቶ አንዳርጋቸው ፅጌ እንዲቀርቡለት የሚያቀርበውን አቤቱታ ተመልክቶ ይገኙበታል ተብሎ ለታሰበው ተቋም ትዕዛዝ ለመስጠት ለጥቅምት 23/2008 ዓ.ም ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡

The post የቃሊቲ ማረሚያ ቤት “አንዳርጋቸው ጽጌ እኔ ጋር የሉም” አለ appeared first on Zehabesha Amharic.

Sport: አንቶኒ ማርሻል –አዲሱ የቀይ ሰይጣኖቹ አለኝታ

$
0
0

antony Marcial

ማንችስተር ዩናይትድ ለአንቶኒ ማርሻል ግዥ 38 ሚሊየን ፓውንድ ሂሳብን ለሞናኮ ሲከፍል ሆላንዳዊው አሰልጣኝ ሉዊ ቫንሃል የእብደት ተግባርን የፈፀሙ ተደርገው በአንዳንዶች ተቆጥሮባቸው ነበር፡፡ ለአንድ የ19 ዓመት ወጣት 36 ሚሊዮን ፓውንድ እጅግ ውድ የሚባል ዋጋ ነው የሚል አስተያየትን የሰጡ ወገኖችም በርካታዎች ሲሆኑ ታይተዋል፡፡ በግሩም የአጨራረስ ብቃት ሁለት ጎሎችን በሳውዝ ሀምፕተን መረብ ላይ ለማሳረፍ መቻሉ ቫንሃል ትክክለኛውን ውጤታማ የአጥቂ መስመር ተጨዋችን ማግኘታቸውን ያረጋገጠላቸው ሆኗል፡፡

ማንችስተር ዩናይትድ በሴንት ሜሪ ስቴዲየም ሳውዝሀምፕተንን 3ለ2 በሆነ ውጤት ለማሸነፍ በቻለበት ግጥሚያ ከመረብ ያሳረፋቸው የመጀመሪያዎቹ ሁለት ግጥሚያዎች በስሙ ያስመዘገቧቸው ጎሎቹን ብዛት ሶት በማድረስ የኦልድ ትራፎርድ የፉትቦል ህይወቱን ባማረ ሁኔታ ለመጀመር ችሏል፡፡ ማርሻል ለማንችስተር ዩናይትድ ሶስቱን የፕሪሚየር ሊግ ጎሎችን ለማስቆጠር የፈጀበት ለ80 ደቂቃዎች ብቻ በሜዳ ላይ መቆየት ነው፡፡

በአንፃሩ ራዳሜል ፉልካኦ ባለፈው ሲዝን ሙሉ ሲዝንን ለማንችስተር ዩናይትድ በስሙ ያስመዘገባቸው ጎሎች ብዛት አራት ብቻ ናቸው፡፡ ይህ የሚያሳየው ሉዊ ቫንሃል ማንም ባልገመተው መልኩ የቡድናቸው ጎሎችን የማስቆጠር ችግርን ሙሉ ለሙሉ ለመቅረፍ ኃይል ያለው አስገራሚ ወጣትን ማግኘት መቻላቸውን ነው፡፡ ከዝውውሩ ወዲህ ማንችስተር ዩናይትድ ሊቨርፑልን 3ለ1፣ እንዲሁም ሳውዝሀምፕተንን 3ለ2 በረታበት ሁለት ተከታታይ የፕሪሚየር ሊግ ግጥሚያዎች ከመረብ ያሳረፋቸው ሁሉም ሶስት ጎሎች በግሩም የአጨራረስ ብቃት ከመረብ የተገናኙ በመሆናቸው በ19 ዓመቱ ፈረንሳዊው ኢንተርናሽናል አጥቂ ብቃት የፉትቦሉ አለም አግራሞቱን በመግለፅ ላይ ነው፡፡

በሴንት ሜሪ በተደረገው ግጥሚያ ሁን ማታ ያስቆጠራት ሌላኛዋ ጎል በሜዳ ላይ የነበሩት ሁሉም የማንቸስተር ዩናይትድ ተጨዋቾችን ባሳተፈ መልኩ በ45 ፓሶች በሜዳ ላይ የነበሩትን ሁሉንም የማንችስተር ዩናይትድ ተጨዋቾችን ባሳተፈ መልኩ ቢሆንም የሁሉም ታዋቂ የፉትቦል ተንታኞችን ልዩ ትኩረት የሳበው ግን አንቶኒ ማርሻል የወጣበት ውድ ዋጋ ምንም አይነት ተፅዕኖ ሳይፈጥርበትና በማንቸስተር ዩናይትድ የፊት አጥቂ መስመር መሰለፍ የሚፈጥረውን ከፍተኛ ጫናን በመቋቋም ከወዲሁ ሶስት የፕሪሚየር ሊግ ጎሎችን ከመረብ ለማሳረፍ መቻሉ ነው፡፡

በማርሻል ዙሪያ አስተያየታቸውን ከሰነዘሩት የፉትቦል ተንታኞች ውስጥ የቀድሞው የሊቨርፑል ዝነኛ ግርሃም ሶውነስ ‹‹ሰፊ ልምድን ከማጣቱ በስተቀር ሁሉንም አይነት ብቃቶችን አሟልቶ የያዘ አስገራሚ ወጣት ሆኖ አግኝቼዋለሁ፡፡ በተለይም ከፍተኛ ፍጥነቱና እውነተኛ የሆነ የሰውነት ጥንካሬን መላበሱ አስገራሚ ሆኖብኛል፡፡ ከሁሉም በላይ ደግሞ እስካሁን ለማንቸስተር ዩናይትድ በተሰለፈባቸው ሁለት ግጥሚያዎች ያደረጋቸው ሶስቱንም አላማቸውን የጠበቁ ጎል የማስቆጠር ሙከራዎችን ከመረብ ማሳረፉ ያማረ የጎል አጨራረስ ብቃትን መላበሱን የሚያሳይ ነው›› በማለት ፈረንሳዊው ወጣት አጥቂን አድንቆታል፡፡

የማንችስተር ዩናይትዱ የቀድሞ ዝነኛ አምበል ጋሪ ኔቭል በበኩሉ ‹‹ሉዊ ቫንሃል ለአንቶኒ ማርሻል ግዥ ውድ ዋጋ መክፈላቸው አስገራሚ ሆኖብኝ ነበር፡፡ ምክንያቱም በአንድ ሲዝን ሌላው ቀርቶ እስከ 15 የሚደርስ ጎልን ማስቆጠሩ አጠራጣሪ ሆኖብኝ ነበር፡፡ በተግባር ያየነው ግን ማርሻል ማንችስተር ዩናይትድን ብዛት ያላቸው ጎሎችን ለማሳፈስ የሚያስችለው ትክክለኛው የአጥቂ መስመር ተጨዋች መሆኑን ነው፡፡ ለዚህ አባባሌ አንዱ ምክንያት የሆነኝ ጎሎችን ካስቆጠረ በኋላ ደስታውን በተጋነነ መልኩ የመግለፅ ባህል የሌለው መሆኑ ነው፡፡ እንደዚህ አይነቱ ባህል ያላቸው ተጨዋቾች ብዙውን ጊዜ የራስ የመተማመን መንፈሳቸው እጅግ ያማረ ሲሆን መታየቱ የተለመደ ነው›› የሚል አስተያየቱን በመሰንዘር ሉዊ ቫንሃል ማርሻልን በዝውውር መስኮቱ መጨረሻ ቀን የገዙበት ተግባራቸውን አድንቆላቸዋል፡፡

(ይህ ስታትስቲክስ ከ3 ሳምንት በፊት የነበረና የትናንት ምሽቱን የቻምፒዪንስ ሊግ ጨዋታ አይመለከትም)

የአንቶኒዮ ማርሻል የእስካሁኑ የሲዝኑ የፕሪሚየር ሊግ የቁጥር መረጃዎች

80- በሜዳ ላይ የቆየባቸው የፕሪሚየር ሊግ ደቂቃዎች

4- ያደረጋቸው አጠቃላይ ጎል የማስቆጠር ሙከራዎች

3- አላማቸውን ያገኙለት የጎል ሙከራዎችና ያስቆጠራቸው የሊጉ ጎሎች

አንቶኒ ማርቫል በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ በተሰለፈባቸው የመጀመሪያዎቹ ሁለት የሊጉ ግጥሚያዎች በእያንዳንዱ ላይ ጎልን በማስቆጠር ታሪክ ሶስተኛው የማን ዩናይትድ ተጨዋች ሆኗል፡፡ ሌሎቹ ሉዊስ ሳህና ፍሬዲሪኮ ሜኬዳ ናቸው፡፡

ማርሻል በእስካኑ ሲዝን ያስቆጠራቸው 3 የፕሪሚየር ሊግ ጎሎች የቼልሲዎቹ ኤደን ሃዛርድ፣ ዲያጎ ኮስታና ፔድሮ በድምሩ በስማቸው ካስመዘገቧቸው ጎሎች ብዛት ጋር እኩል ናቸው፡፡

The post Sport: አንቶኒ ማርሻል – አዲሱ የቀይ ሰይጣኖቹ አለኝታ appeared first on Zehabesha Amharic.

ከእስር የተለቀቁት የዞን 9 ጦማርያን እና ጋዜጠኞች ምስጋና አቀረቡ

$
0
0

(ዘ-ሐበሻ) በቅርቡ ግማሹ ክሱ ተቋርጦ; አንዳንዶቹም በነጻ ሌላው በዋስ የተፈቱት የዞን 9 አባላት ምስጋናቸውን አቀረቡ:: ከዞን 9 አባላት የተሰጠውን የምስጋና ቃል እንደወረደ እነሆ:-

እናመሰግናለን

በድንገት ከያለንበት ተይዘን እንደታሰርነው አፈታታችንም ግራ የሚያጋባ ነበር፡፡ ተመሳሳይ ክሶች ቀርበውብን እያለ ግማሾቻችን ‹ክስ ተቋርጦላችኋል› ተብለን ተፈታን፣ ግማሾቻችን ደግሞ ‹ነፃ ናችሁ› (ከሳሽ በነፃነታችን ላይ ይግባኝ መጠየቁ እንዳለ ሁኖ) ተብለን ይሄው ወጥተናል፡፡ ቀሪ ክስ ይዘን በዋስ ወጥተን እየተከራከርንም ያለን አለን፡፡ በዚህ ሁሉ መሃል የሁላችንም ዕምነት ግን አንድም ቀን ሊያሳስረን የሚገባ ወንጀል አለመፈፃችን ማመናችን ነው፡፡ መፈታታችን ጥሩ ሁኖ፤ መታሰር በፍፁም የማይገባን ነበርን፡፡ መፃፋችን እና ሕግ እንዲከበር መጠየቃችን ሀገሪቱ አገራችን እንድትሻሻል እና ሁላችንም ዜጎች የተሻለ ህይወት አንዲኖራቸው ከመሻት ባለፈ ሌላ ነገር አልነበረውም/የለውም፡፡ ነገር ግን ይህን በማድረጋችን ተገርፈናል፣ ተዘልፈን-ተሰድበናል፣ ታስረናል ተሰደናልም፡፡ ይህ በፍጹም አይገባንም ነበር፡፡
zone9
የእኛ መታሰር ፖለቲካዊ ንቃት የፈጠረላቸው ሰዎች እንዳሉ ሲነግሩን ደስ ይለናል፡፡ በእኛ መታሰር ምክንያት ለመጠየቅና ለመፃፍ በጣም እንደሚፈሩ የሚነግሩን ሰዎች ስናገኝ ደግሞ እናዝናለን፡፡ የመታሰራችን ጉራማይሌ ስሜት እንደዚህ ነው፡፡ ሳይገባን በመታሰራችን የነቁ መኖራቸውን በማወቃችን የምነደሰተውን ያክል፤ ሳይገባን በመታሰራችን የተሰበሩና ከተዋስኦ መድረኩ የራቁ እንዳሉ ስናውቅ እጅግ እናዝናለን፡፡

መታሰር በደል ነው፡፡ ብዙ ነገር ያጎድላል፡፡ መታሰር መልካም ነው፡፡ ብዙ ነገር ያስተምራል፡፡ እኛ በመታሰራችን ሀገራችን የበለጠ እንድናውቃት ሁነናል፡፡ ሀሳብን በነፃነት የመግለፅ ነፃነት አሁንም ብዙ ዋጋ እንደሚያስከፍል ተረድተናል፡፡ ሕግን መከታ አድርገው የኖሩ ‹ስም የለሽ› ዜጎች ሕጉ ሲከዳቸውና እነሱ ላይ ‹በላ› ሲያመጣባቸው ታዝበናል፡፡ ከሁሉም በላይ ፍትህ የሌለባት ሀገር ለዜጎቿ የማትመችና አገር እንደሆነች አይተናል፡፡
በእስራችን ወቅት የተለያዩ በደሎች በተቋም ደረጃ ደርሰውብናል፡፡ ግን አገር ነውና ከይቅርታ የሚያልፍ አይደለም፡፡ ለበደላችሁን አካላት እናንተ ይቅርታ ባትጠይቁንም፤ እናንተ የፈለጋችሁትን ባለማድረጋችንና ሕግን መሰረት አድርገን በመኖራችን ስላስከፋናችሁ እባካችሁ ይቅር በሉን፡፡

በዚህ ሁሉ መሃል ግን እናንተ አላችሁ፡፡ ጓደኞቻችንም ናችሁ፤ ዘመቻ አድራጊዎችም ናችሁ፤ ቤተሰቦቻችንም ናችሁ፤ ጠያቂዎቻችንም ናችሁ፤ ጠበቆቻችንም ናችሁ፣ የመንፈስ አጋሮቻችንም ናችሁ ርቀት ሳይገድባች የጮሃችሁልን አለም አቀፍ የመብት ጠያቂዎችም ናችሁ … በመታሰራችን የተረዳነው አንዱ ትልቅ ነገር የናንተን መልካምነት፣ የናንተን አጋርነት እና የናንተን የማይሰለች ድካምና ፍቅር ነው፡፡ እናንተ ባትኖሩ ‹አጭሩ› የእስር ጊዜያችን ይረዝምብን ነበር፤ ‹ቀላሏ› እስር ትከብድብን ነበር፡፡ ምስጋና ለናንተ፤ እስራችን ‹አጭር› – ፈተናችን ‹ቀላል› እንዲሆን አድርጋችሁልናልና፡፡
እናንተ ወዳጆቻችን ለሁሉም ነገር – እልፍ ምስጋና

እናመሰግናለን!
የዞን9 ጦማርያን እና ጋዜጠኞች

The post ከእስር የተለቀቁት የዞን 9 ጦማርያን እና ጋዜጠኞች ምስጋና አቀረቡ appeared first on Zehabesha Amharic.


በሚኒሶታ የ14 ዓመት ልጁን ጥሎ ሕይወቱ ያለፈው ኢትዮጵያው ቀብር ነገ ቅዳሜ ይፈጸማል

$
0
0

(ዘ-ሐበሻ) ካለ እናት እርዳታ ላለፉት 14 ዓመት ብቸኛው ልጁን ሲያሳድግ የቆየው ደረጀ ካሳዬ ድንገት ሕይወቱ ማለፉን ተከትሎ ለዚህ ህፃን ልጅ የወደፊት ሕይወት ማቃኛ ይሆን ዘንድ የገቢ ማሰባሰብ እየተደረገ ይገኛል::

የደረጀ ካሳዬ የቀብር ስነስርዓት ነገ በሚኒሶታ እንደሚፈጸም አስተባባሪዎቹ የገለጹ ሲሆን ሁሉም ኢትዮጵያዊና የኢትዮጵያውያን ወዳጆች በመገኘት እንዲሸኙት ጥሪ ቀርቧል:: የቀብሩ ቦታን የሚገልጸው መረጃ ከዚህ ቀጥሎ ቀርቧል:: ከታች ደግሞ የሟችን ልጅ ለመርዳት ለምትፈልጉ መረጃውን አቅርበናል::
Funeral_Dereje1
(ዘ-ሐበሻ) ካለ እናት ለብቻው ነበር ይህን ወጣት ላለፉት 14 ዓመታት ያሳደገው:: ደረጀ ካሳዬ:: ከቀናት በፊት ኦክቶበር 19 የ46 ዓመቱ ደረጀ ድንገት ሕይወቱ በዛው አለፈች:: የ14 ዓመቱ ልጅም ካለ እናትም ካለ አባትም ብቻውን ቀረ:: ይህ ልጅ ወደ ፎስተር ኬር መሄድ ይችላል ግን እኛ ኢትዮጵያውያን ለምን ዝም እንላለን?? ቀጣዩን መል ዕክት ያንብቡ:;
ወንድማችን ደረጄ ካሣዬ በ September 16, 1969 በአዲስ አበባ ከተማ ተወልዶ በ October 19, 2015 በተወለደ በ 46 ዓመቱ በሚኖርበት በሴንት ፖል ሚኒሶታ በድንገት ሕይወቱ አልፏል።
አቶ ደረጄ ካሳዬ ከኢትዮጵያ ለኑሮ ወደ አሜሪካ ከ14 ዓመት ታዳጊ ወጣት ልጁ ጋር ከመጣ ዓመት ባልበለጠው ጊዜ ባልተጠበቀ ሁኔታ መታመሙ እንኳ ሳይታወቅ በተኛበት ሞቶ ተገኝቷል።
የሚያሳዝነው ነገር ቢኖር ገና የአንድ ዓመት ህጻን እያለ እናቱን በሞት ተነጥቆ በአባቱ እንክባቤ ብቻ ላደገው ታዳጊ ወጣት ያለምንም እናት ያሳደገውን ውድ አባቱን በድንገት ማጣቱ እጅግ በጣም አሳዝኖናል።
የቀብር ሥርዓቱን ለማስፈጸምና የልጁንም የወደፊት ህይወት መስመር ለማስያዝ የሁላችንም ድጋፍና ትብብር አስፈላጊ በመሆኑ ሁላችሁም ወገናዊ ድጋፋችሁን በመግለጽ የእርዳታ እጃችሁን ትዘረጉ ዘንድ ጥሪያችንን ስናቀርብ ከታላቅ አክብሮት ጋር ነው።
እርዳታዎን በሚከተለው የኢንተርኔት አድራሻ በመግባት መለገስ ይችላሉ
https://dm2.gofund.me/es6w6ysc

 

dereje

The post በሚኒሶታ የ14 ዓመት ልጁን ጥሎ ሕይወቱ ያለፈው ኢትዮጵያው ቀብር ነገ ቅዳሜ ይፈጸማል appeared first on Zehabesha Amharic.

ደራሲ ይስማዕከ ወርቁ ተከሰሰ * የፊታችን ሰኞ ፍርድ ቤት ይቅረብ ተብሏል [አለምነህ ዋሴ ያነበዋል]

$
0
0


“ዴርቶጋዳ” በተሰኘው የመጀመሪያ ረዥም ልብወለዱ ዕውቅና ያተረፈው ደራሲ ይስማዕከ ወርቁ፤ በአይናለም የመጽሐፍት መደብር ባለቤት፣ በአቶ አይናለም መዋ የ330 ሺህ ብር ክስ እንደቀረበበት ምንጮች ጠቆሙ፡፡ ከክስ መዝገቡ ላይ ለመረዳት እንደተቻለው፤ ደራሲ ይስማዕከ ወርቁ “ዴርቶጋዳ” እና “ዣንቶዣራ” የተሰኙ መጽሐፎቹን በራሱ ማተሚያ ቤት አሳትሞ ለአይናለም መዋ ለመስጠት ከተዋዋለ በኋላ፣ ውሉን አፍርሶ ከሌላ ሰው ጋር ተዋውሏል፡፡ አይናለም የመፅሀፎቹን ዋጋ አስቀድሞ መክፈሉም በክሱ ተጠቅሷል፡፡ ደራሲው መጽሐፎቹን አትሞ ለመስጠት የተዋዋለው እስከ ሰኔ 4 ቀን 2007 ዓ.ም ድረስ የነበረ ቢሆንም “ዴርቶጋዳ” የተሰኘውን መጽሐፍ 5ሺህ ኮፒ አሳትሞ ለመስጠት ተዋውሎ 2ሺህ ኮፒ ብቻ ለውል ሰጪው በማድረስ ቀሪውን 3ሺህ ኮፒ ለሌላ ሰው ከውል ውጪ ማስተላለፉ በክሱ ላይ ተገልጿል፡፡
ደራሲ ይስማዕከ ወርቁ ተከሰሰ * የፊታችን ሰኞ ፍርድ ቤት ይቅረብ ተብሏል [አለምነህ ዋሴ ያነበዋል]
ክሱ የቀረበለት ፍ/ቤትም፤ ተከሣሽ ቀርቦ ምላሽ እንዲሰጥ ለፊታችን ሰኞ ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡ ደራሲና አሣታሚ ይስማዕከ ወርቁ በበኩሉ፤ ስለክሱ የሚያውቀው ነገር እንደሌለ ለአዲስ አድማስ በስልክ በሰጠው ምላሽ ገልጿል፡፡ አስራ አንደኛ መፅሀፉን ለማውጣት በማስተዋወቅ ላይ የሚገኘው ዝነኛው ደራሲ ይስማዕከ፤ “ዴርቶጋዳ” የተሰኘ የመጀመሪያ ልብወለዱ ከ200ሺ በላይ ቅጂዎች እንደተሸጡለት ይታወቃል፡፡ የሙሉ ጊዜ ደራሲ የሆነው ይስማዕከ፤ በአዋሳ የህክምና ትምህርቱን አጠናቋል፡፡
Source: Addis Admass Newspaper

The post ደራሲ ይስማዕከ ወርቁ ተከሰሰ * የፊታችን ሰኞ ፍርድ ቤት ይቅረብ ተብሏል [አለምነህ ዋሴ ያነበዋል] appeared first on Zehabesha Amharic.

የአርቲስት ሠብለ ተፈራ ባለቤት ክስ ተመሰረተበት

$
0
0

sebele tefera
(ዘ-ሐበሻ) በአዲሱ ዓመት የመጀመሪያው ቀን ሞገስ ተስፋዬ እያሽከረከረ የነበረው መኪና ከቆመ መኪና ጋር በመጋጨቱ የአርቲስት ሰብለ ተፈራ ሕይወት ማለፉ ይታወሳል:: በወቅቱም አቶ ሞገስ ሙዚቃ ለመቀየር ስል ነው የተጋጨሁት ሲል ለፖሊስ ቃል መስጠቱን ዘ-ሐበሻ ዘግባ ነበር:: ዛሬ ከአዲስ አበባ የተሰማው ብስራት ራድዮ የሰብለ ተፈራ ባለቤት ክስ ተመሰረተበት ይለናል:: ዝርዝሩን ያድምጡ::

The post የአርቲስት ሠብለ ተፈራ ባለቤት ክስ ተመሰረተበት appeared first on Zehabesha Amharic.

5 ብሔር ተኮር ነፃ አውጪ ግምባሮች በጋራ የነፃነት እና የዴሞክራሲ ንቅናቄ መሠረቱ

$
0
0

(ዘ-ሐበሻ) በኦስሎ ኖርዌይ ከኦክቶበር 22 እስከ ኦክቶበር 23, 2015 ዓ.ም በተደረገ የጋራ ጉባኤ 5 የኢትዮጵያ የብሄር ድርጅቶች በጋራ ለመታገል አዲስ ንቅናቄ መመስረታቸውን ለዘ-ሐበሻ በላኩት መግለጫ አስታወቁ::
olf ONLF
ጥምረቱን የመሰረቱት የቤኒሻንጉል ነፃ አውጪ ንቅናቄ; የጋምቤላ ነፃ አውጪ ንቅናቄ; የኦጋዴን ነፃ አውጪ ግምባር; የኦሮሞ ነፃነት ግምባርና የሲዳማ ብሔራዊ ነፃነት ግምባር ሲሆኑ የኢትዮጵያ ያለውን ስርዓት በጋራ ጥለው የሁሉንም ብሄሮች የራስን ዕድል በራስ የመወሰን መብት የሚያከብርና የአንድን ቡድን የበላይነት እንዲያበቃ የሚያደርግ ስርዓት ለመፍጠር እንደሚታገሉ በመስራች ጉባኤያቸው መጨረሻ ላይ ባወጡት መግለጫ አስታውቀዋል::

ሃገሪቱን ወደ ተሻለ የፖለቲካ ሽግግር ቀርጸው ለመንቀሳቀስ የተሰማሙት እነዚሁ 5 ድርጅቶች የአዲሱ ጥምረታቸው መጠሪያ የሕዝቦች ጥምረት ለነፃነትና ለዴሞክራሲ (Peoples Alliance for Freedom and Democracy (PAFD) ተብሎ ተሰይሟል::

(በእንግሊዘኛ ቋንቋ የተሰጠውን መግለጫውን ለማንብብ እዚህ ይጫኑ)

አርበኞች ግንቦት በቅርቡ ከአማራው ንቅናቋ; ከአፋር ንቅናቄና ከትግራይ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ ጋር በጋራ ለመታገል ጥምረት መፍጠሩ ይታወሳል:: ትናንት በኖርዌይ ጥምረታቸውን ያወጁት የቤኒሻንጉል ነፃ አውጪ ንቅናቄ; የጋምቤላ ነፃ አውጪ ንቅናቄ; የኦጋዴን ነፃ አውጪ ግምባር; የኦሮሞ ነፃነት ግምባርና የሲዳማ ብሔራዊ ነፃነት ግምባር ከአርበኞች ግንቦት 7 ጋር ወደፊት ስለሚፈጥሩት የጋራ ጥምረት ወይም ግንኙነት ይኑራቸው አይኑራቸው የተገለጸ ነገር ባይኖርም በቅርቡ ወደ ሚኒሶታ የመጡት የንቅናቄው የውጭ ጉዳይ ኃላፊ አቶ ነአምን ዘለቀ “ኢትዮጵያ የምትባል ሃገር እንዳለች እስካመኑ ድረስ ከሁሉም ጋር በጋራ ለመስራት እንችላለን::” ማለታቸውን ዘ-ሐበሻ መዘገቧ አይዘነጋም::
ONLF and OLF

The post 5 ብሔር ተኮር ነፃ አውጪ ግምባሮች በጋራ የነፃነት እና የዴሞክራሲ ንቅናቄ መሠረቱ appeared first on Zehabesha Amharic.

Sport: ሎዛ አበራ ለኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ዛሬ ያስቆጠረቻቸውን 2 ጎሎች ይዘናል (Video)

$
0
0

‪በፓፓ‬ ኒው ጊኒ አስተናጋጅነት ለሚካሄደው የአለም ከ20 ዓመት በታች የሴቶች እግር ኳስ ሻምፒዮና አፍሪካን ወክሎ ለመሳተፍ የኢትዮጵያ ከጋና ጋር ባደረጉት ጨዋታ 2-2 በአቻ ውጤት ተያይተዋል። ሁለቱንም ጎሎች ያገባችው የ2014 የኢትዮጵያ ሴቶች ኮከብ ጎል አግቢ የሆነችው ሎዛ አበራ ናት:: ጎሎቿን ይመልከቱ:: የመልሱ ጨዋታ ከሁለት ሳምንት በኃላ አክራ ጋና ይደረግና በደርሶ መልሱ አጠቃላይ ውጤት አሸናፊው አገር አፍሪካን ወክሎ በአለም ዋንጫ የሚሳተፍ ይሆናል።

u20 ethiopia
loza

The post Sport: ሎዛ አበራ ለኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ዛሬ ያስቆጠረቻቸውን 2 ጎሎች ይዘናል (Video) appeared first on Zehabesha Amharic.

ከፖለቲካው በስተጀርባ ያሉት እውነቶች –ከተማ ዋቅጅራ

$
0
0

TPLF 2
ክፍል ፩

ወያኔ በመጀመሪያ እቅዱን ቀርጾ ሲንቀሳቀስ የነበረበት ትግራይን ነጻ ለማውጣት የሚል ነበረ። በዚህ ግልጽ ባልሆነ በተደበቀ አላማቸው እውነተኛ ኢትዮጵያዊ የሆኑትን የትግራይ ተወላጆችን አታለውበታል። ከዓላማቸው በስተጀርባ ተንኮላቸውን ደብቀው በቋንቋቸው የትግራይ ተወላጆችን በመቀስቀስ ወደ ትግሉ ጎራ በብዛት እንዲገቡ በማድረግ ህዝቡ የማያውቀውን አላማ በመጫን በህዝብ ላይ ታላቅ ደባ ሰርተውበታል። ህይወትን በሚያክል መሰዋትነትን በሚጠይቀው ትግል ውስጥ ሲገባ ታጋዩ የሚታገልበትን አላማ ሊያውቀው ይገባል አታጋዮችም የተነሱበትን አላም በግልጽ ለታጋዩ እና ለህዝብ ማሳወቅ ይኖርባቸዋል። ወያኔዎች የትግላቸውን ዓላማ ከጥቂቶች በስተቀር በታጋዩም ሆነ በህዝቡ ዘንድ አይታወቅም በዚህ የተነሳ እርስ በራሳቸው ይበላሉ ነበረ። ሚስጢራቸውን ያወቀውንም ሆነ ለማወቅ የሚፈልገውን አልያም ክትትል የሚያደርጉት ታጋዮችን በአስር ሺዎች የሚቆጠሩትን በረሃ ላይ አጥፍተዋቸዋል። አሁን የያዙትን ስልጣን ለመያዝ በሚያደርጉት ትግል ከደርግ ጋር በመዋጋት ከሞተው የትግራይ ተወላጅ በራሳቸው ሰዎች ምስጢራችንን አወቁብን ምስጢራችንን ሊያውቁ ነው ምስጢራችንን እንዳያወጡብን በማለት አላማችን ከሚጠፋ እነሱ ይጥፉ እያሉ በወያኔ ሰዎች የተገደሉት የትግራይ ታጋዮች ከደርግ ጋር በነበረው ጦርነት ከሞቱት በአስር ሺዎች የበለጠ እንደሚሆን ለወያኔ ቅርበት ያላቸው የትግል አጋሮቻቸው የነበሩ የትግራይ ተወላጆች ይነግሩናል። ግዜው ሲደርስ ሁሉም እውነታዎች ፍንትው ብለው ይወጣሉ እንደታፈነ የሚቀር ምንም ነገር የለም። ታዲያ ወያኔ የታገለው ለማን ነው? የትግሉስ አላማ ምንድን ነበረ?

የወያኔ የትግል እና የደርግ ትግል ሌላኛው ገጹ የአሜሪካ እና የሩሲያ ጦርነት ሊባል ይችላል። ኃይሌ ገብረስላሴ እና ፖልቴርጋት ሲዲኒ ላይ በተደረገው የኦሎፒክ ውድድር የአስር ሺ ሜትር ሩጫ ሲያደርጉ ኬኒያዊው ፖልቴርጋት የናይክ ካንፓኒ ትጥቅ አድርጎ ኢትዮጵያዊው ኃይሌ ገብረስላሴ የአዲዳስ ካንፓኒን ትጥቅ አድርገው ይሮጣሉ ፉክክሩም በጣም ከባድ ነበረ በመጨረሻውም ኃይሌ አንገት ላንገት ተናንቀው በመግባት ፖልቴርጋትን አሸንፎታል። እናም ሚዲያዎች በኢትዮጵያዊው ኃይሌ እና በኬንያዊው ፖልቴርጋት የተደረገ ውድድር ሳይሆን በናይክ እና በአዲዳስ ካንፓኒዎች ጭምር ውድድሩ እንደተደረገ አድርገው ያቀርቡ ነበረ። እንደዚሁ ሁሉ ከወያኔ ጀርባ አሜሪካ እና እንግሊዝ ከደርግ ጀርባ ደግሞ ሩሲያ ነበረች። በአሜሪካ እና በእንግሊዝ ከፍተኛ ድጋፍ ታግዘው በነዚሁ አገሮች የስለላ መረብ ተዘርግቶላቸው በለስ ቀንቷቸው ወያኔ ወደ ስልጣን ወንበር ወጡ። በሌላ አገላለጽ በኢትዮጵያ ጉዳይ ላይ አሜሪካ እና እንግሊዝ በሪሲያ ላይ የበላይነታቸውን አሳዩ እንደማለትም ሊሆን ይችላል።

የደርግ ወታደር በጦርነት ተሸንፎ ስልጣኑን አላስረከበም ይሄንን ሁሉም ኢትዮጵያዊ ያውቀዋል። አሁን እንኳን ሰራዊቱ የመሰባሰብ እድሉን ቢያገኝ ወያኔዎችን መግቢያ እና መውጫ ቀዳዳ እንደሚያሳጣቸው ይታወቃል ምክንያቱም ወያኔ ማለት አገር ሻጭ አገር ከፋፋይ እንደሆኑ የኢትዮጵያ ህዝብ ስላወቃቸው በጽናት ስለሚታገላቸው የቀደመው አይነት ክፍተት አይፈጠርም። የደርግ ሽንፈት የእግዚአብሄር ጉዳይ ነው እንጂ የወያኔ የጦር የበላይነት አይደለም። ደርግ አንባ ገነን ቢሆንም ቅሉ ስርአቱ መለወጥ እንዳለበት ቢታወቅም ቅሉ እንደ ወያኔ በጥላቻ እና በዘር በሃይማኖት መከፋፈል የአንድ ብሄር የበላይነት አንግሶ የሚዘርፍና የሚጨቁን ሳይሆን ኢትዮጵያን ሁሉ እንደ አንድ የሚያይ በማንም ላይ የዘር ጥላቻ ስለሌለው ከዳር እስከዳር አንድ አድርጎ የሚገዛ ነበረ። ሰራዊቱ የህዝብ ፍቅር ስላለው መሳሪያችሁን ጥላችሁ ወደ ቤተሰቦቻችሁ ተቀላቀሉ ሲባሉ በየዋህነት ያንን አድርጎ ነው ወደ ቤተሰቡ የተቀላቀለው እንጂ በህዝብ ላይ ያደረሰው ጉዳት የለም። ያ ባይሆን ኖሮ ግን ወያኔ እንደዚ አገር አፍራሽ እና አገር ሻጭ እንደሆነ ሰራዊቱ ቢያውቅ ኖሮ መቼም የአሁኑን ስልጣን አይዙም ነበረ። የደርግ ወታደር የኢትዮጵያ ወታደር ነበረ። የደርግ ስርአቱ ቢለወጥም ወታደራዊ ተቋሙ መፍረስ አልነበረበትም ምክንያቱም ያ ሰራዊት ወታደራዊ ስልጠናዎችን በኢትዮጵያ ህዝብ ሃብት የተማሩ ትልልቅ የወታደር ተቋም ካላቸው አገር እንደ ሩሲያ፣ አሜሪካ እና እስራኤል ባሉ አገራት ወታደራዊ ትምህርታቸውን በብቃት የተከታተሉ የወታደ ኢንጅነሮች የነበሩበት ተቋም ስለነበር። ታዲያ ይህ ጠንካራ ወታደራዊ ተቋም አፍሪካን መግዛት ይችላል እየተባለ በሃያላን አገራት ጭምር ይነገርለት የነበረው ወታደራዊ ኃይል እንደት ወያኔ እና ሻቢያ የተባሉትን ማጥፋት አቃተው? ቢባል ደርግ በፈጠረው ከፍተኛ የሆነ አንባ ገነንነት አቋሙ ተጠቅመው ድብቅ የሆነውን አጀንዳቸውን መፈጸም በመቻላቸው ነው። ሌላው ደግሞ አሜሪካም ሆነች እንግሊዝ በአፍሪካ ጠንካራ የወታደር ተቋም ያውም የነሱን ፖሊሲ የማይደግፍ በአፍሪካ አገር እንዲቋቋም ያለመፈለጋቸው ነው። ወያኔዎች በነዚህ አገራት ከፍተኛ የሆነ የስለላ ስራ እና ትጥቅና ስንቅ እርዳታ ጭምር በከፍተኛ ድጋፍ የማግኘታቸው ጉዳይ ነው። ሌላው ከፍተኛ ስልጣን ያላቸው እና ቁልፍ ቦታ የሚባለው ወታደራዊ ቦታዎችን የሚመሩትን የደርግ ባለስልጣን ለወያኔ መስራታቸው ነው። ትልቁም የደርግ ውድቀት ወያኔ ጀግና ሆኖ ሳይሆን የደርግ ባለስልጣን ወታደራዊ ሚስጢርን አሳልፈው በመስጠታቸው ነው።

ሽንፈቱም የራሱ በሆኑት በከፍተኛ ማእረግ እና ቁልፍ ወታደራዊ ቦታ በሃላፊነት ተሰጥቶአቸው የተሳሳተ ትህዛዝ እየሰጡ ምስኪኑን ለአገሩ የሚታገለውን ወታደር እያስፈጁ በተከበበ የጠላት ክልል ውስጥ መሃል እንዲገባ ትእዛዝ እየሰጡ ያስፈጁት ነበረ። ሌላው ቀርቶ የጦር ሄሊኮፕተር ጭምር አስልከው የወያኔ ምሽግ እና ወታደሮችን ሳይሆን የራሳቸውን ወታደር ሲጨፈጭፉ የነበሩት። የደርግ ወታደራዊ መዋቅር በብቃት የተመሰረተ ነው። መከላከያዉ በእዞች እዞች በክፍለ ጦሮች ክፍለ ጦሮች በሻለቆች ሻለቆች በሻንበሎች እያለ የተከፋፈለ እና በተዋረድ የሚወርድ ጠንካራ መዋቅር ነበረው።ጠንካራ አየር ኃይል ጠንካራ ባህር ኃይል ጠንካር ምድር ጦር የነበረው ያውም በዘመድ ሳይሆን በብቃት የተመለመሉ ብቃት ያላቸው ጀግና ወታደሮች የተሸነፈው በወያኔ ሳይሆኑ አምኖ በሾማቸው የራሱ ሰዋች ናቸው።

የደርግ ሃይል ከፍተኛ ቁጥር ያለው ወታደር በኤርትራ ተቀምጦ ነበር። ይሄ የሆነበት ምክንያት ሁሉም ነገር ወደ ሰሜን ግንባር የሚለውን አዋጅ ተከትሎ ነው። ሰሜን የሰፈረውን ኃይል ድጋሜ ሌላ ትዕዛዝ በመስጠት ወደ ሸዋ እንዲንቀሳቀስ አድርገውታል። ይህ የሚደረገው ከአንድ ቦታ ተነስቶ ወደ ሌላ ቦታ እንቅስቃሴ በሚያደርግበት ግዜ በጠላት አስከብቦ ወታደሩን ለማስጨረስ ነው። በሁሉም ግንባር ላይ ቦታችሁን ለቃችሁ ሂዱ ጠላት በከፍተኛ ሁኔታ ያላው በዛኛው ግንባር ነው እያሉ የያዙትን ቦታ በበላይ አዛዞቻቸው ትዕዛዝ ወሳኝ የሚባሉትን ቦታዎች በቀላሉ ወያኔ እንዲይ ያደርጉ ነበረ የወያኔ ወታደሮችም ጫካ ውስጥ ጥይታቸውን እያንጣጡ በመንገድ ጠራጊዎች በደርግ ባለስልጠን እየተመሩ በፍጥነት ወደ መሃል አገር መጓዝ ጀመሩ። ቀድመው ለስብሰባ ተብለው ከአገር እንዲወጡ የተደረጉት መንግስቱ ኃይለማሪያም ከአገር በወጡ በጥቂት ቀናት ውስጥ አዲስ አበባን በመቆጣጠር ደርግ ሲቆጣጠርበት የነበረውን የኢትዮጵያ ቴሌቪዝን እና ራዲዮ የኢህአዴግ ሰራዊት ተቆጣጥሮታል ብለው በቴሌቪዝንም በሬድዮም በመናገራቸው ሰራዊቱ መሳሪያውን በመጣል ወደ ቤተሰቡ ለመቀላቀል ችሏል። ጀግና ሳይሆኑ መጀገኑ ዋጋ የለውም አሸናፊ ሳይሆኑ አሸናፊ መባሉ እርባና አይኖረውም እድል ቀንቷት ቅል ድንጋይ ልትሰብር መጣሯን እያየን ነው። ቅል ድንጋይ መስበሯን ወደፊት እናየዋለን ወይ ቅልነቷን አውቃ ትቀመጣለች አልያም እራሷን ከድንጋይ ጋር አጋጭታ እራሷን በራሷ ትሰብራለች።

ወያኔ ስልጣን ከያዘ በኃላ ድብቅ ማንነቱን ያየንበት ነው። ይሄ ማንነቱ ምን ይመስላል ለሚለው እና ሌሎች ተያዝነት ያላቸውን እውነታዎችን በክፍል ሁለት ይቀጥላል።
ከተማ ዋቅጅራ
22.10.2015
Email-waqjirak@yahoo.com

The post ከፖለቲካው በስተጀርባ ያሉት እውነቶች – ከተማ ዋቅጅራ appeared first on Zehabesha Amharic.

የኢትዮጵያና ኤርትራ ቅራኔዎች 

$
0
0

Pro. Minga Negash

ከሚንጋ ነጋሽ

የኢትዮጵያና የኤርትራ ጥናቶች ብዙ ጊዜ የሚያተኩሩት፤እንደ ሌሎቹ አፍሪካን የሚመለከቱ ጥናቶች ሁሉ ከነፃነት በፊትና በሁዋላ ስለተፈጠሩ መንግስታትና የፖለቲካ ኢኮኖሚ ስርአት፤ ስለምዐራብያወያን የቀኝ ግዛት ፍለጋ ዘመቻዎችና፤ እንደዚሁም በነዚህ ሀገሮች ዉስጥ ስለሚኖሩ ሰዎች ባህልና ቁዋንቁዋ ነዉ። የፕሮፌሰር ያን አቢንክን የ2010 የኢትዮጵያ-ኤርትራ ጥናቶች ዝርዝር የተመለከተ፤ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ማለትም ከ1995 እስከ 2010 የተሰሩትን ስራዎች ርዕሶች፤ ፀሀፊዎቹንና ጽሁፎቹ የወጡበትን ቦታ፤ጥራትና ተአማኒት፤ እንደዚሁም ከነዚህ ስራዎች የወጣዉን የእዉቀት መሰረትና መዋቅር (philosophical base & intellectual structure) ለመገምገም እድል ይሰጣል። ከዚህም በተጨማሪ የምርምር ርአስ ምርጫ፤የጥናቱን የመነሻ ሀሳብ መሰረት፤ የምርመር መንገድ ምርጫ (research design)ና የሚደርሱበትን ድምዳሜ መፈሽ በተለይ ለአዲስ ተመራማሪዎች ይጠቅማል። ይህ ግን የረጅም ጊዜ ስራ ይጠይቃል። በበቂ መረጃና ጽንሰ ሃሳብ ያልተፈተሸ  ብሄራዊ ፖሊሲ ዉሎ አድሮም ቢሆን ችግር መፍጠሩ አይቀርም። ብሄራዊ የሆኑ ጉዳዮችን በተለያዩ የእዉቀት መነፅሮችና፤ የልምድ ተመክሮዎች መፈተሽ ወደ ተሻለ የፖሊሲ ንድፈ ሃሳብ እንደሚያሸጋግር ይታወቃል። በዚህም መሰረት ይህ ጽሁፍ የኢትዮጵያንና የኤርትራን ቅራኔዎች በሌላ መነጽር ለማየት ይሞክራል። ለዚህም ያለዉን ነባራዊ ሁኔታ ነፃና ሚዛናዊ በሆነ ልቦና መገንዘብ ያሰፈልጋል። ይህ ጽሁፍ ብዙ ታሪካዊ ማጣቀሻዎች ስላሉት – እዚህ ጋር ተጭነው በPDF ያንብቡ

The post የኢትዮጵያና ኤርትራ ቅራኔዎች  appeared first on Zehabesha Amharic.


Sport: ሜሲ!!! የእግርኳሱ መሲህ

$
0
0

 

UEFA Champions League 2014/15 Round of 16 Second Leg Barcelona v Manchester City Camp Nou, Barcelona, Spain - 18 Mar 2015

ባርሴሎና ባለፈው በቻምፒዮንስ ሊጉ ሮም ኦሎምፒክ ላይ ከሮማ ጋር 1-1 በተለያየበት ጨዋታ ሊዮኔል ሜሲ በቀዩ እና ሰማያዊው ማልያ 100ኛ የቻምፒዮንስ ሊግ ጨዋታውን ፈፅሟል፣ አርጀንቲናዊው በውድድሩ 80 ጎሎችን ካስቆጠረው ክርስቲያኖ ሮናልዶ ቀጥሎ በ77 ጎሎች ሁለተኛ ደረጃ ላይ ተቀምጧል፡፡

አራት ጊዜ የቻምፒዮንስ ሊግ ዋንጫዎችን ያነሳው የ27 ዓመቱ ሜሲ የመጀመሪያ ድሉ በ2009 በሮም ኦሎምፒኮ ያሳካው ነበር፣ በጨዋታው ሊዮኔል ከዣቪ ኸርናንዴዝ የተሸጋገረለትን የአየር ላይ ኳስ ወደ ጎልነት ለውጦ ቡድኑን አሸናፊ አድርጓል፤ ጨዋታውም 2-0 ተጠናቅቋል፡፡

በ2011 ባርሴሎና ማንችስተር ዩናይትድን 3-1 በረታበት ጨዋታ ሜሲ አንድ ጎል አስቆጥሯል፣ በዌምብሌይ ኳስ እና መረብን ያገናኘው አጭሩ አጥቂ በተጠናቀቀው የውድድር ዘመን ቡድኑ በተመሳሳይ ጁቬንቱስን 3-1 ሲያሸንፍ ጎል ማስቆጠር አልቻለም፡፡

ሊዮ ባርሴሎና በ2006 በፓርክ ደ ፕሪንስ አርሰናልን 2-1 አሸንፎ ከ1992 በኋላ ታላቁን ዋንጫ ሲያነሳ የቡድኑ አባል የነበረ ቢሆንም በግማሽ ፍፃሜው በደረሰበት ጉዳት ምክንያት ሳይሰለፍ ቀርቷል፡፡

የአራት ጊዜ የወርቅ ኳስ ተሸላሚው የሆነው ኮከብ በቻምፒዮንስ ሊጉ ለመጀመሪያ ጊዜ የመሰለፍ ዕድል ያገኘው ዲሴምበር7 2007 ባርሴሎና በዶኔስክ ከሻክታር ጋር ባደረገው ጨዋታ ነበር፣ አሰልጣኝ ፍራንክ ራይካርድ ቀድሞ ከምድብ ማጣሪያ ማለፉን ያረጋገጠውን ቡድን በቋሚ ተሰላፊዎች ከመጠቀም ይልቅ አዳዲስ ፊቶችን ለመመልከት በነበረው ፍላጎት ሜሲን ከተጠባባቂ ወንበር አንስቶ ለማጫወት እቅድ ነደፈ፣ የካታላኑ ክለብም በጨዋታው 2-0 ለመሸነፍ ተገደደ፡፡

ሊዮ በቻምፒዮንስ ሊጉ የመጀመሪያ ጎሉን ያስቆጠረው ኖቬምበር 2/2005 ነበር፣ በኑካምፕ ባርሴሎና የግሪኩን ፓናቲናይኮስን 5-0 በረታበት ጨዋታ ሶስተኛውን ጎል አግብቶ በታላቁ መድረክ የጎል አካንቱን ከፈተ፡፡

በቻምፒዮንስ ሊጉ 100ኛ ጨዋታውን የፈፀመው የግራ እግሩ አጥቂ በውድድሩ አምስት ጊዜ ኮከብ ጎል አግቢ ሆኖ ሲፈፅም 48 ጎሎችንም አስቆጥሯል፤ ይህ በሁለት ጨዋታ አምድ ጎል የማስቆጠር ያህል ተደርጎ ሊወሰድ ይችላል፡፡

በአንድ ጨዋታ ሁለት ጎሎችን ያስቆጠረባቸው ጨዋታዎች 16 ደርሰዋል፤ በሶስት አጋጣሚዎች ሃትሪክ ሰርቷል፡፡ ከምንም በላይ በ2010/11 የውድድር ዘመን ግማሽ ፍፃሜ ሪያል ማድሪድ እንዲሁም በተጠናቀቀው የውድድር ዘመን ባየርን ሙኒክ ላይ በኑ ካምፕ ያስቆጠራቸውን ሁለት ጎሎች መቼም ቢሆን አይዘነጋም፡፡

በዚህ ሂደት ውስጥ ተጨማሪ የማይረሳቸው አጋጣሚዎች ተከስተዋል፡፡ በ2011/12 የውድድር ዘመን ሁለተኛው ዙር ላይ ባርሳ ባየር ሌቨርኩሰን ላይ ሰባት ጎሎችን ሲያስቆጥር (ጨዋታው 7-1 ተጠናቅቋል) ሜሲ አምስት ጎሎችን አግብቶ ነበር፣ ባለፈው ዓመት የሻክታር ዶኔስኩ አጥቂ ሉዌስ አድሪያኖ በባቴ ቦርሶቭ ላይ ተመሳሳይ የጎል መጠን እስኪያስቆጥር ድረስ የባርሴሎናው ልጅ ሪከርዱን በብቸኝነት ይዞ ነበር፡፡

በ2009/10 የውድድር ዘመን በቻምፒዮንስ ሊጉ በአንድ ጨዋታ ለመጀመሪያ ጊዜ በርካታ ጎሎችን ያስቆጠረበት ወቅት ነበር፡፡ በኢምሬትስ ከአርሰናል ጋር 2-2 የተለያየው ባርሳ በኑካምፕ የሰሜን ለንደኑን ክለብ 4-1 ሲያሸንፍ የላ ሜሲያው ግኝት የተጋጣሚ ቡድን ተከላካዮችን እጅግ በጣም አሰቃይቶ አራቱንም ጎሎችን አስቆጥሯል፡፡ ይህንን ሲፈፅም እግርኳስን ተንከባክቦ እና ውበትን ጨምሮ ተጫውቷል፡፡

‹‹ሊዮኔል በእያንዳንዱ ጨዋታ ላይ መሰለፍ ይፈልጋል›› ይላል ከ2008-2010 ድረስ በባርሴሎና አብሮት የተጫወተው አጥቂው ቲዮሪ ሆንሪ፣ ‹‹በኮፓ ዴል ሬይ ከመጀመሪያው ዙር ጀምሮ እስከ ፍፃሜው ድረስ መጫወት ይሻል፡፡ በልምምድ ሜዳ ላይ እንኳን ማሸነፍ እንጂ ሽንፈት አይፈልግም፡፡ በአንድ የጨዋታ እንቅስቃሴ ጥፋት ከተፈፀመበት ከራሱ ግብ ጠባቂ ኳስ እንዲሰጠው በትህትና ጠይቆ ከፊቱ የሚገኙትን ተጨዋቾች በሙሉ አልፎ ኳስ እና መረብን ማገናኘት ይፈልጋል፡፡ ተጋጣሚው ጎል በማስቆጠር በድጋሚ ጨዋታውን ሲጀምር ድንገት ኳስ ይነጥቅና ተጨማሪ ጎል ያገባል፣ የእርሱ ቡድን እስኪያሸንፍ ድረስ ይህንን ደጋግሞ ይፈፅማል፡፡ የዚህ አይነት ተጨዋች ከዚህ ቀደም ገጥሞኝ አያውቅም››

በእርግጥም ሜሲ የእግርኳስ ‹‹ሊቅ›› ነው፣ ኧረ እንዲያውም በህይወት ዘመን አንድ ጊዜ የሚገኝ ታላቅ ተጨዋች መሆኑ አያጠያይቅም፡፡ ብቃቱ ማቆሚያ ያለው አይመስልም፣ እርሱን የሚያውቁ ይህንን ይመሰክራሉ፣ ነገሩ የተጋነነ አይደለም፣ የተጋነኑ የሚመስሉ አስተያየቶችን መስጠትም ፍትህን ማዛባት አይሆንም፡፡

‹‹የፕላኔታችን ምርጡ ተጨዋች›› የሚል ማሞካሻን ያገኘው እንዲሁ አይደለም፣ እስካሁን በነበረው የእግርኳስ ህይወት የነበረው የሜዳ ላይ እንቅስቃሴ እና ሪከርዶቹ ከግምት ውስጥ ገብተው ነው፣ የዚህ ሁሉ ምስጢር ምን ይሆን?

‹‹ሪከርዶቼን ወደ ኋላ መለስ ብዬ አልመለከትም፤ አሁንም ድረስ እግር ኳስን እየተጫወትኩኝ የምገኘው ለዚህ ነው፡፡ እርግጥ ነው በእኔ ቦታ ላይ የሚጫወት የትኛውም ተጨዋች ጎሎችን ማስቆጠር ይሻል፤ የእኔ ቀዳሚ ግብ ዋንጫዎችን ማንሳት ነው፡፡ ሁልጊዜም ቢሆን የሚያነሳሳኝ ዋንጫ ነው፤ ዋንጫዎችን ማንሳት ተነሳሽነት ይፈጥርብኛል፤ እንደ ቡድን ከዚህ የተሻለ ነገር ማግኘት አይቻልም›› ይላል፡፡

በዚህ ደረጃ የሚገኝ ተጨዋች ከግል ሽልማት ይልቅ በቡድን ለሚገኝ ስኬት ቅድሚያ ሲሰጥ መመልከት ያስደስታል፡፡ ተጨዋቹ በ90ሺ ወይም 90 ተመልካቾች ፊት ቢጫወት ሁልጊዜም ቢሆን ቅድሚያ የሚሰጠው ዋንጫዎችን ለማንሳት ነው፡፡

‹‹ተነሳሽት ለማግኘት አልቸገርም፤ እግርኳስን መጫወት እወዳለሁኝ፤ በልምምድ ሜዳ ላይ መገኘት ያስደስተኛል፡፡ በዚህ አይነት መልኩ በየዕለቱ የማሳልፈው ነገር ደስታ ይሰጠኛል፤ አንድ ስኬት ስታገኝ ተጨማሪ ድሎችን ደጋግመህ ማሳካት ትፈልጋለህ›› የሚል አስተያየትን የሚሰጠው ኮከብ ‹‹ልምምድም ይሁን ጨዋታ አልያም ዋንጫዎችን ማንሳት ያስደስተኛል፡፡ ምርጡ ህይወቴ እነኚህ ናቸው፡፡ ሁልጊዜም ቢሆን ከቡድኔ ጋር ዋንጫዎችን ማንሳት እፈልጋለሁኝ፤ በቃ ይኸው ነው›› ይላል፡፡

‹‹ወርልድ ክላስ›› ተጨዋቾችን ከሌሎች መደበኛ ተጨዋቾች የሚለያቸው የድል ረሃብ ስሜታቸው ነው፤ በየጊዜው ዋንጫዎችን ለማንሳት ያላቸው ፍላጎት በድል ላይ ድል እንዲደግሙ ያስችላቸዋል፡፡

እርግጥ ነው 2014 ለሜሲ አስደሳች አልነበረም፡፡ በላ ሊጋው የመጨረሻ ጨዋታ አትሌቲኮ ማድሪድን የማሸነፍ ግዴታ ውስጥ የገባው ባርሴሎና 1-1 ተለያይቶ በመጨረሻም ዋንጫውን ተነጥቋል፤ በቻምፒዮንስ ሊጉ በዲያጎ ሲሞኒ ቡድን ሩብ ፍፃሜ ላይ ሽንፈትን አስተናግዶ ረጅም ርቀት መጓዝ አልቻለም፣ በዓለም ዋንጫው ደግሞ አርጀንቲና በፍፃሜው ጨዋታ በጀርመን 1-0 ተሸንፋ ከ1986 በኋላ ይህንን ዋንጫ ለማንሳት የነበራት ዕድል ሳይሳካ ሲቀር ሊዮ በግሉ ከፍ ያለ ትችት አስተናግዷል፡፡

2015 ዓመት ግን የእርሱ ነበር፡፡ በግልም ሆነ እንደ ቡድን ከፍ ያለ ስኬትን አስመዝግቧል፡፡ ‹‹በዓለም ዋንጫ ለፍጻሜ ቀርቦ ሽንፈትን ማስተናገድ ጥሩ የሆነ ስሜትን አይፈጥርም፣ ለአገሬ ታላቁን ዋንጫ ማስገኘት እፈልግ ነበር፡፡ ነገር ግን እንደ ፕሮፌሽናል እግር ኳስ ተጨዋች ከመጥፎ አጋጣሚ በማገገም ወደፊት መጓዝ ተገቢ ነው›› የሚል አስተያየትን ሰጥቶ ‹‹እንደ እግርኳስ ተጨዋች ሽንፈትን ካስተናገድክ በኋላ በቀጣይ የሚገጥምህን ፈተና በብቃት በመወጣት መጥፎውን አጋጣሚ መርሳት ምርጥ አማራጭ ነው፤ የዓለም ዋንጫው መጥፎ አጋጣሚ ጥሩ ስሜት እንደማይፈጥር ግልፅ ነው፡፡ ነገር ግን ብስጭቱ ለድል ያነሳሳይል፡፡

ሊዮ የተናገረውን ነገር በተጠናቀቀው የውድድር ዘመን በሚገባ ተግባራዊ አድርጓል፡፡ የላ ሊጋውን ዋንጫ ለማንሳት ባልተቸገረው ባርሴሎና ሜሲ በርካታ ጎሎችን አስቆጥሯል፡፡ የኮፓ ዴል ሬይ ዋንጫን ለማንሳት አልተቸገረም፡፡ ከምንም በላይ በበርሊን ጁቬንቱስን 3-1 አሸንፎ ሻምፒዮን ሆኗል፤ በእነኚህ ድሎች የአጭሩ ኮከብ አስተዋፅኦ ከፍ ያለ ነበር፡፡

ለባርሴሎና ያለፈው ዓመት አስደሳች ነበር፤ ለሁለተኛ ጊዜ የሶስትዮሽ ዋንጫ ባለቤት በመሆን በስፔን ብቸኛው ክለብ ሆኗል፡፡ በ2009 በፔፕ ጋርዲዮላ እንዲሁም ባለፈው ዓመት በሉዊስ ኤንሪኪ ይህንን ስኬት ሊጎናፀፍ ሊዮ የሁለቱም ቡድን መሪ ተዋናይ ነበር፡፡

እርግጥ ነው በባርሴሎና ያለፈው ዓመት ታሪካዊ ስኬት አርጀንቲናዊውን ብቻ አጉልቶ መጥቀስ ሌሎቹን መናቅ ይሆናል፤ ሉዊስ ሱዋሬዝ ከብዙ ውጣ ውረድ በኋላ ታላቅነቱን አስመስክሯል፡፡ በቻምፒዮንስ ሊጉ የፍፃሜ ጨዋታ ጭንቀት ላይ ለነበረው የካታላኑ ክለብ ኳስ እና መረብን አገናኝቶ ቡድኑን ከጭንቀት መገላገሉ እንዴት ይረሳል? ሶስተኛውን ጎል አግብቶ የቡድኑን አሸናፊነት ያረጋገጠው ኔይማርስ እንዴት ይዘነጋል?

ሶስቱ አጥቂዎች ባለፈው ዓመት በሁሉም ውድድሮች በጋራ 119 ጎሎችን አስቆጥረዋል፡፡ ይህ አስገራሚ ሪከርድ ነው፤ በላ ሊጋው 81 ጎሎችን አግብተዋል፡፡ ባየርን ሙኒክ በተመሳሳይ ወቅት በቡድን ደስ ሊጋው 80 ጎሎችን አግብቷል፤ የፕሪሚየር ሊጉ ሻምፒዮን ቼልሲ 73 እንዲሁም የሴሪ አው አሸናፊ ጄቬንቱስ 70 ጎሎችን አስቆጥረዋል፡፡

‹‹በጣም ዕድለኛ ነኝ›› ይላል- ሊዮ፣  ባለፈው ዓመትም ከታላቅ አጥቂዎች ጎን ተሰልፎ ተጫውቻለሁኝ- ከሮናልዲንሆ ጋር ድንቅ የሆነ መግባባት ነበረኝ፡፡ ከእርሱ በኋላ ደግሞ ከሳሙኤል ኤቶ፣ ቲዮሪ ሆንሪ፣ ፔድሮ፣ ዴቪድ ቪያ እና አሌክሲስ (ሳንቼዝ) ጎል ተሰልፌ በመጫወት አስደሳች ጊዜያትን አሳልፌያለሁኝ፡፡

‹‹ከምንም በላይ ከኔይማር እና ሱዋሬዝ ጋር የፈጠርኩት ጥምረት የተለየ ነው፤ ሁለቱ አጥቂዎች የብቃታቸው ጫፍ ላይ ይገኛሉ፡፡ በጋራ የተጫወትነው ለአንድ ዓመት ብቻ ቢሆንም ጥምረታችን በጣም ይገርማል፡፡ በቀጣይ ከዚህ የተሻለ ጥምረት መፍጠር እንደምንችል አልጠራጠርም፡፡ ቅድሚያ የምንሰጠው ለቡድን ሥራ ነው፡፡ ኔይማር ባለው ኳሊቲ፣ የኳስ ንክኪ እና አካል ብቃት የዓለማችን ምርጡ ተጨዋች መሆን ይችላል፡፡ ሉዊስ (ሱዋሬዝም) ተመሳሳይ ነው፤ የኳስ ቁጥጥሩ፣ እይታው፣ እንቅስቃሴው፣ ደሙ ነፍሳዊ አጨዋወቱ በአጠቃላይ የማይታመን ነው፡፡ ሁላችንም የተለያዩ ግብአቶችን እናበረክታለን››

ምናልባት አሁን ባለው ሁኔታ ከሜሲ ቀድመው ሊቀመጡ የሚችሉት ፔሌ እና ዲዮጎ ማራዶና ብቻ ሊሆኑ ይችላሉ፡፡ ከ2003 ጀምሮ ለባርሴሎና መሰለፍ የጀመረው ይህ ኮከብ ዕድሜው ገና 27 መሆኑን አምኖ መቀበል ያስቸግራል፡፡

ስኬቱን ልዩ የሚያደርገው ዘመናዊው እግርኳስ በአካል ብቃቱ ረገድ ወደላቀ ምዕራፍ መሸጋገሩ፣ ታክቲካዊ ጉዳዮች ትኩረት የሚሰጣቸው መሆኑ፣ ክፍተቶችን ማግኘት አስቸጋሪ እየሆነ መምጣቱ እንዲሁም መከላከል ላይ ማተኮሩ ነው፡፡ ያም ቢሆን ሁሉም ነገር ለዚህ ተጨዋች ከባድ አልሆነም፡፡

በዚህ ዘመን ለፈጣሪ ተጨዋቾች ከፍተትን ማግኘት ፈታኝ ቢሆንም ሜሲ ግን ሳይቸገር የሚፈልገውን ነገር በመፈፀም ላይ ይገኛል፡፡ ኧረ  እንዲያውም ከእያንዳንዱ ጨዋታ ስኬት አልፎ አራት ጊዜ የወርቅ ኳስ በማግኘት በግሉ ሪከርዱን በእጁ አስገብቷል፡፡

ባለፉት 11 ዓመታት ለባርሴሎና እና አርጀንቲና በጋራ 311 ጨዋታዎች ፈፅሟል፤ በስድስት ትልልቅ ውድድሮች ላይ ተሳታፊ ሆኗል፡፡ በእነኚህ ጊዜያት 591 ሺ 626.4 ማይል ተጉዟል፤ በአራት የተለያዩ አህጉት 1061 ሰዓታት በርሯል፡፡ በአጠቃላይ 44 ቀናት በጉዞ አሳልፏል፡፡ በሌላ አነጋገር መሬትን 23.9 ጊዜ ዞሯል፡፡

‹‹የብራዚሉ ሮናልዶ የልጅነት አርአያዬ ነበር፣ ለባርሴሎና እና ብራዚል የማይታመን ነገር ሰርቷል፡፡ ከእርሱ የበለጠ ተሰጥኦ የታደለ አጥቂ አልተመለከትኩም፣ የሚገርም ተሰጥኦ ባለቤት ነው፤ ሁሉም ሰው ይህንን መመልከት ይችላል፣ ከምንም ነገር ተነስቶ ጎሎችን ያስቆጥራል፣ የሚያደርጋቸውን ሙከራዎች አስገራሚ ነበሩ፡፡ ከሜዳ ውጭም ቢሆን ድንቅ ሰው ነበር፤ ዚኔዲን ዚዳንንም መጥቀስ አለብኝ፤ እርሱ ሲጫወት መመልከት ያስደስተኝ ነበር፡፡ የፈረንሳውያን ጀግና ነው፤ ከሜዳ ውጭም ቢሆን በአስደናቂ ስብዕና አለው›› የሚለው ሜሲ ነው፡፡

በኤንሪኬ ዘመን ሜሲ የቦታ ለውጥ አድርጓል፡፡ ወደ ኋላ ተመልሶ በአማካይ ቦታ ላይ እስከመሰለፍ ደርሷል፤ ሜሲን ወደፊት በአማካይ ቦታ ላይ ለመጫወት እቅድ አለህ? የሚል ጥያቄን ስታነቡበት ‹‹አዎን፤ ይህ እንደሚቻል ይሰማኛል፤ በርካታ ተጨዋቾች ዕድሜያቸው እየገፋ ሲሄድ ወደኋላ ተመልሰው ይጫወታሉ፤ በቀጣይ ወደ ኋላ ተመልሼ የአማካይ ስፍራ ተጨዋች እንደምሆን ይሰማኛል፤ ከወዲሁ በአማካይ ቦታ በመጫወት በአማካይ ቦታ ላይ በመጫወት በርካታ ቦታዎችን አካልያለሁኝ፤ እንደ አጥቂ በፊት መስመር ላይ መጫወት ያስደስተኛል፤ በርካታ አጥቂዎች በጥልቀት ወደኋላ ተመልሰው በአማካይ ቦታ ላይ በመጫወት የእግር ኳስ ህይወታቸውን ያራዝማሉ፤ ሁልጊዜም በሩጫ ላይ የተመሰረተ አጨዋወት መከተል አይቻልም የሚል ምላሽ ይሰጣል፡፡

ከላ ሊጋ ክለቦች ሊዮ የፔፕ ጋርዲዮላውን ባየርን ሙኒክ መመልከት ያስደስተዋል፤ ‹‹ፔፕ ሁልጊዜም አዳዲስ ነገሮችን ይሞክራል፤ ይህ ለእግርኳስ አስደሳች ነገር ነው፤ በአውሮፐ አዳዲስ ነገሮችን መፍጠር በጣም ያስደስታል›› የሚል አተያየትን ሰጥቶ ‹‹እርሱን በተቃራኒ ወንበር ላይ ሲቀመጥ መመልከት የእንግዳ ስሜትን ይፈጥራል፤ በእግርኳስ ህይወቴ ስሜትን ይፈጥራል፤ በእግርኳስ ህይወቴ ላበረከተው አስተዋፅኦ በጣም ላመሰግነው እወዳለሁኝ፤ ሆኖም የእርሱን ቡድን በተቃራኒ ስገጠም የማስበው ማሸነፍን ብቻ ነው›› ይላል፡፡

የሜሲ ተሰጥኦ የዳበረው በልምምድ እንደሆነ ግልፅ ነው፤ ከባርሴሎና ተጨዋቾች መሀከል በልምምድ ሜዳ ላይ ታታሪው ማነው? የሚል ጥያቄ ስታስተከትሉበት ‹‹ይህንን መናገር ይከብዳል፤ ሆኖም ዣቪ እና ኢንዬስታን ማስቀደም አለብኝ፤ ለረጅም ዓመታት የዚህክለብ ልብ ሆነው ቆይተዋል፡፡ በልምምድ ሜዳ እንደ እነርሱ አይነት ታታሪ ተጨዋቾች አልተመለከትኩም›› በማለት ይመልሳል፡፡

The post Sport: ሜሲ!!! የእግርኳሱ መሲህ appeared first on Zehabesha Amharic.

Sport: ማንቸስተር ዩናይትድ ከማንቸስተር ሲቲ – [ስታትስቲክስ –የቡድን ዜናዎች –ግምት –ጠቃሚ መረጃዎች]

$
0
0

key Battle
ከኤሊያና ሔኖክ

የ እንግሊዝ ፕሪምየር ሊግ በዓመቱ ከሚጠበቁ አጓጚ ጨዋታዎች መካከል አንዱ የማንቸስተር ደርቢ ነው:: ማን.ዩናይትድ ከማንችስተር ሲቲ ከሰዓታት በኋላ በትያትር ኦፍ ድሪምስ ይፋለማሉ:: በማንቸስተር ከተማ ከፍተኛ የሆነ የፖሊስ ጥበቃ አለ – ምክንያቱም ደጋፊዎች ከጨዋታ በፊትም ሆነ በኋላ በሚያደርጓቸው አለመግባባቶች ከዚህ ቀደም በርከት ያለ ንብረት ጠፍቷልና ነው:: ዘ-ሐበሻ ይህን የማንቸስተር ደርቢን በማስመልከት የቡድኖቹን ፕሪማች (ከጨዋታ በፊት) ያሉትን ዜናዎች; መረጃዎች እና ስታስቲክሶች ታስቃኛችኋለች – መልካም ንባብ::

የጉዳት ዜናዎች:

ከማንቸስተር ዩናይትድ በኩል በዚህ ጨዋታ አሽሊ ያንግና ሉክ ሻው በጉዳት የማይሰለፉ ሲሆን ከሲቲ በኩል ዴቭድ ሲልቫ; ሰርጂዮ አጊዮሮ; ጋኤል ክሊሺ እና ሳሚር ናስሪ አይሰለፉም:: አምበሉ ቬንሰንት ኮምፓኒም በዚህ ጨዋታ ላይሰለፍ ይችላል እየተባለ ነው::

አሰልጣኞቹ ምን አሉ?

የማንቸስተር ዩናይትዱ አለቃ ልዊስ ቫንገሃል “የመጣሁት ከትንሽ መንደር ነው:: በዚያ መንደር ውስጥ ስለ ኳስ እጅጉን ይወራል:: በማንቸስተር ከተማ ግን ይለያል – ወሬው ስለዚህ ጨዋታ ነው:: ደጋፊዎች በጣም ስሜታዊ ሆነው ብዙ ነገሮችን ሲያደርጉ ይታያል:: ሲቲ በጣም ጠንካራና በፕሪምየር ሊጉ ካሉ ግምት ከሚሰጣቸው ቡድኖች ውስጥ አንዱ ነው:: ይህን ጨዋታ ማሸነፍ ለኛ ትልቅ ነገር ነው” ብለዋል ከጨዋታው በፊት በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ::

የማንቸስተር ሲቲው አሰልጣኝ ማኑኤል ፔሊግሪያኒ “ከማንቸስተር ዩናይትድ ጋር የምናደርገው ይህ ጨዋታ 6 ነጥብ ጨዋታ አድርጌ ነው የምወስደው:: ይህ ጨዋታ ከተቀናቃኝህ/ተከታይህ ጋር የምታደርገው ፍልሚያ ነው:: ግን የዚህ ጨዋታ ውጤት የሲዝንን አሸናፊ ይለያል ማለት አይደለም:: ሲቲ በጥሩ አቋም ላይ እንገኛለን – ፕሪምየር ሊጉን እየመራን ነው (አርሰናል ለጊዜው ይዞታል ዛሬ ቦታውን) – ይህ ማለት ጥሩ እንሆናለን ማለት ሳይሆን ከጨዋታ ጨዋታ ስህተቶቻችንን እያየን እናስተካክላለን ለማለት ነው:: በዚህ ትልቅ ጨዋታ ስህተት አለመስራት ትልቁ ግባችን ነው” ብለዋል ከጨዋታው በፊት በሰጡት አስተያየት::

ግምት – ማን ያሸንፋል?

ታዋቂው የቢቢሲ ስፖርት ተንታኝ ማርክ ላውረንሰን ይህን ጨዋታ ማን ያሸንፋል? ሲል የራሱን ግምት ሰጥቷል:: ይህን ተከትሎም በዓለም አቀፍ ደረጃ ቁማሩም ደርቷል:: ማርክ ላውረንሰን በሰጠው ግምት ሲቲ ሰርጂዮ አጉዬሮን እና ዴቭድ ሲልቫን ሳይዝ ገብቶ ማን.ዩናይትድን ያሸንፋል ብዬ አላስብም ብሏል:: እንደ ማርክ ላውረንሰን ግምት ይህ ጨዋታ በአቻ ውጤት ይጠናቀቃል::

እስካሁን ማን አሸነፈ?

ባለፉት 8 የፕሪምየር ሊግ ደርቢ ጨዋታዎች ሲቲ 6ቱን አሸንፏል:: ሲቲ ይህን ጨዋታ ካሸነፈ 50ኛውን ድል በማን.ዩናይትድ ላይ በመቀዳጀት ደስታውን እጥፍ ድርብ ያደርጋል::

ግምታዊ አሰላለፍ

ግምታዊ አሰላለፍ

ስታትስቲክስ:
ማንቸስተር ዩናይትድ ልዊስ ቫንገሃል ከያዙት ወዲህ ከ23ቱ የባለፉት ጨዋታዎች ውስጥ 17ቱን አሸንፏል:: 3 ጊዜ አቻ ሲወጣ የተሸነፈው 3 ጊዜ ነው::
ማን.ዩናይትድ ይህን ጨዋታ ካልተሸነፈ ከ2010 ወዲህ ለመጀመሪያ ጊዜ በሜዳቸው በ5 የመጀመሪያ የመክፈቻ ጨዋታዎች ባለመሸነፍ ሪከርዳቸውን ያሻሽላሉ::
ዋይኒ ሩኒ 30ኛ ዓመቱን ይህ ጨዋታ ከመደረጉ አንድ ቀን በፊት ደፍኗል:: ይህ አጥቂ 187 የፕሪምየር ሊግ ጎሎችን በማግባት በስሙ አስመዝግቧል:: ሩኒ በማንቸስተር ደርቢ ላይ 11 ጎሎችን በማግባት ብቸኛው የዩናይትድ አጥቂ ነው::

ማን.ሲቲ በዚህ ሲዝን በርካታ ጎሎችን ካገቡ የፕሪምየርሊጉ ክለቦች መካከል ቀዳሚውን ቦታ ይይዛሉ:: 24 ጎሎችን ያስቆጠሩ ሲሆን 11ዱን ጎሎች ያገቡት ባለፉት ሁለት ጨዋታዎች ነው::
ማኑኤል ፔሊግሪያኒ የሚያሰለጥኑት ሲቲ ባለፉት 18 ጨዋታዎች ጎል ሳያስቆጥር አልወጣም::

ዘግየት ያሉ መረጃዎች ዴቭድ ሲልቫ በዚህ ደርቢ ጨዋታ ላይ የሚያሰልፈው ጤንነት ላይ ይገኛል ይላሉ::

እርስዎ ማን ያሸንፋል ይላሉ?

ግምትዎን ይስጡ

 

The most-eagerly awaited fixtures in the city’s football calendar, Manchester City and Manchester United have been playing each other since 1881. The first clash of the Reds and Blues’ 2014-15 season will be the 168th time they’ve met.

The post Sport: ማንቸስተር ዩናይትድ ከማንቸስተር ሲቲ – [ስታትስቲክስ – የቡድን ዜናዎች – ግምት – ጠቃሚ መረጃዎች] appeared first on Zehabesha Amharic.

በበዓሉ ግርማ ግድያ ዙሪያ አዲስ መረጃ ወጣ – [አለምነህ ዋሴ ያነበዋል]

መምህር በጋሻው ተሞሸረ

$
0
0

begashaw

begashaw 23
(ዘ-ሐበሻ) በኢየሩሳሌም ከወራት በፊት በቅዱስ ቁርባን ጋብቻውን ፈጽሞ የነበረው መምህር በጋሻው ደሳለኝ በዛሬው ዕለት በአዲስ አበባ በሠርግ ከወ/ት ንፁህ አስፋው ጋር ተሞሽሯል::

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን መዝሙሮች መግቢያ ላይ እንዲሁም በተለያዩ ትምህርቶቹ እውቅና ያለው መምህር በጋሻው ከባለቤቱ ጋር ከዚህ ቀደም በኢየሩሳሌም በቤተክርስቲያናዊ ስነስርዓት ስጋ ወደሙን ተቀብለው ስርዐተ ተክሊላቸዉን ከፈጸመ በኋላ ዛሬ በአዲስ አበባ ሠርግ የደገሰው ወዳጅ ዘመዶቹን ለማመስገን እንደሆነ ታውቋል::

The post መምህር በጋሻው ተሞሸረ appeared first on Zehabesha Amharic.

Sport: ራሂም ስተርሊንግ ‹‹በማንችስተር ሲቲ ስኬታማ እንደምሆን እርግጠኛ ነኝ››

$
0
0

 

Raheem sterling

‹‹በዘመናዊ ፉትቦል እጅግ ተፈላጊው የአጥቂ መስመር ተጨዋች ነው›› በማለት የማንችስተር ሲቲው አሰልጣኝ ማኑኤል ፔሌግሪኒ የገለፁት በ49 ሚሊዮን ፓውንድ ከሊቨርፑል የገዙትን የ20 ዓመቱን እንግሊዛዊ ራሂም ስተርሊንግን ነው፡፡ በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ውድድርና በማንችስተር ሲቲ ታሪክ የውድ ዋጋ ግዥ የሆነው ስተርሊንግ በበኩሉ በአዲሱ ክለቡ ከሚገኑ ወርልድ ክላስ ፉትቦለሮች ጋር አብሮ ለመሰለፍ ያለው ጉጉት በእጅግ ከፍተኛ መሆኑን ያረጋገጠበት መግለጫን ሰጥቷል፡፡

ለበርካታ ሳምንታት የሚዲያውን ሰፊ ትኩረትን ስቦ የዘለቀው ስተርሊንግ ከአንፊልድ ወደ ኢትሃድ ያደረገው ዝውውር ሙሉ ለሙሉ ተፈፃሚ የሆነው ተጨዋቹ ከማንችስተር ሲቲ የቀረበለት 180 ሺ ፓውንድ ሳምንታዊ የደመወዝ ክፍያን ለመቀበል ፈቃደኛ በመሆኑ ነው፡፡ ማንቸስተር ሲቲ የአቡዳቢ ባለሀብቶች በሚመሩት ሼክ መንሱር ባለቤትነት በ2008 ከተገዛ ወዲህ ለስተርሊንግ የከፈለውን ጨምሮ ባለፉት ሰባት ዓመታት ውስጥ በአጠቃላይ ለ467 ተጨዋቾች ግዢ በድምሩ 719.1 ሚሊዮን ፓውንድ ሂሳብ አውጥቷል፡፡

በሼክ መንሱር ባለቤትነት 46ኛው የተጫዋች ግዥ ውልን የፈረመው ስተርሊንግ ለቀድሞው ክለቡ ሊቨርፑል በ129 ግጥሚያዎች ከተሰለፈ በኋላ ወደ ማንቸስተር ሲቲ ለማምራት የወሰነበት ዋነኛ ምክንያቱ ሊቨርፑል ባቀረበለት የተጨማሪ ዓመታት ኮንትራት ውል ሊሰጠው ባቀደው 100 ሺ ፓውንድ የሳምንት ደመወዝ ደስተኛ ባለመሆኑ ነው፡፡ ሆኖም ግን ስተርሊንግ ለማንቸስተር ሲቲ በይፋ በመፈረም በተቃራኒው አቅጣጫ ወደ ሊቨርፑል በነፃ ዝውውር የሄደው ሌላው እንግሊዛዊው ኢንተርናሽል ጀምስ ሚልነር ይለብሰው የነበረው 7 ቁጥር ማሊያን ከተረከበ በኋላ በሰጠው መግለጫው ዝውውሩን ያደረገበት ዋነኛ ምክንያቱ በሜዳ ላይ ካለው ፉትቦሉ ጋር የተያያዘ መሆኑን ለማመልከት ሞክሯል፡፡

‹‹የዝውውር ውሉ ከሚጠበቀው ጊዜ ቀደም ብሎ ተፈፃሚ በመሆኑ ከፍተኛ የሆነ የደስታ መንፈስን አሳድሬያለሁ፡፡ ይህ ለእኔም ሆነ ለቤተሰቤ አባላት በጠቅላላ ትልቅ እፎይታን የፈጠረልን ጉዳይ ሆኗል›› ያለው ስተርሊንግ በመቀጠልም ‹‹ከሁሉም በላይ የእኔን ከፍተኛ ትኩረትን የሳበው በርካታ ኳሊቲ ያላቸው ፉትቦለሮች የሚገኙበት የማንቸስተር ሲቲ ጠንካራ ስኳድ አንዱ አባል መሆን መቻሌ ነው፡፡ በስኳዱ የሚገኙት አብዛኛዎቹ ተጨዋቾች ከዚህ በፊት የትላልቅ ውድድሮች የዋንጫ ሽልማቶችን የማግኘት ሰፊ ልምድን ያካበቱ በመሆናቸውም በማንችስተር ሲቲ ቆይታዬ እጅግ ተደናቂ ስኬትን ለማስመዝገብ እንደምችል እርግጠኛ ነኝ፡፡ በእንግሊዝ ብሔራዊ ቡድን ካምፕ ለመጨረሻ ጊዜ በተገኘንበት ወቅት ጆ ኸርት የማንቸስተር ሲቲ ስላለው አጠቃላዩ እውነታ ምንነትን በጥንቃቄ አስረድቶኛል፡፡

በተለይ የማንችስተር ሲቲ ደጋፊዎች ተደናቂነቱን ሲነግረኝ ወደዚህ ክለብ የመምጣት ውሳኔዬን እንድገፋበት ምክንያት ሆኖኛል፡፡ ወደዚህ እጅግ ትልቅ ክለብ ለመምጣት የቻልኩት ከኪው.ፒ.አር አንስቶ ለበርካታ ዓመታት ፉትቦሌን ወደ ትልቅ ደረጃ ለማሸጋገር ሳደርገው በዘለቅኩበት ያለሰለሰ ጥረት ፍሬያማ ሆኜ በመሆኑ በራሴ ኩራትን የማላሳድርበት ምክንያት አይኖረኝም፡፡ ስኬታማ እንድሆን ከጎኔ ባለመለየት ከፍተኛ የሆነ ድጋፍን ሲያደርጉልኝ ለዘለቁት ባለሙያዎች በጠቅላላ ያለኝ ምስጋናም ከፍተኛ ነው፡፡

በተለይም ራፋ ቤኒቴዝ ገና በ15 ዓመት ዕድሜዬ ለሊቨርፑል እንድፈርም በማድረግ ትልቅ ውለታን ሰርተውልኛል፡፡ ምክንያቱም ከኪውፒአር ወደ ሊቨርፑል መሸጋገር አጠቃላዩ የፉትቦል ህይወቴን ወደ ትልቅ ደረጃ ለማሸጋገር የቻልኩበትን መሰረትን ያመቻችልኝ ሆኗል፡፡ ከዛ በኋላም ኬኒ ዳግሊሽ ለሊቨርፑል ዋናው ቡድን በመደበኛ ቋሚ ተሰላፊነት የመጫወት እድልን ሰጥቶኝ ሌላኛውን ትልቅ ውለታን አበርክተውልኛል፡፡

ብሬንዳን ሮጀርስም ለእኔ ብቃት ሙሉ እምነትን አሳድረው በመዝለቃቸው በዚህ አጋጣሚ ላመሰግናቸው እወዳለሁ፡፡ በተለይም ሮጀርስ ከማንቸስተር ሲቲ ጋር በተደረገው ግጥሚያ ለመጀመሪያ ጊዜ ለሊቨርፑል ዋናው ቡድን በመደበኛ ቋሚ ተሰላፊነት የመጫወት ዕድልን በመስጠት መላው ዓለም ምርጥ ብቃቱን ለማየት እንዲችል ትልቅ አስተዋፅኦን ስላበረከቱልኝ ከልብ ላመሰግናቸው እወዳለሁ፡፡ በአጠቃላይ የሊቨርፑል ቆይታዬም ችሎታዬን ወደ ትልቅ ደረጃ ለማሸጋገር የቻልኩበት በመሆኑ ለክለቡ ደጋፊዎችና አባላት የሚኖረኝ ክብር ከፍተኛ ሆኖ ይዘልቃል፡፡ ተስፋ የሚደረገውም የሊቨርፑል ደጋፊዎች ይህንን ዝውውርን ለማድረግ እንድወስን ምክንያት የሆነኝ ጉዳይ ምን እንደሆነ ጠንቅቀው ይረዱታል ብዬ ነው›› የሚል አስተያየቱን አክሏል፡፡

ስተርሊንግ ለሊቨርፑል ለመጨረሻ ጊዜ የተሰለፈበትን የ2014/15 ሲዝንን ያሳለፈው በ35 ግጥሚያዎች ተሰልፎ 7 ጎሎችን ብቻ በማስቆጠር ነው፡፡ ይህንን ከግንዛቤ በማስገባት በርካታ አስተያየት ሰጪዎች ማንቸስተር ሲቲ ለ20 ዓመቱ እንግሊዛዊ ኢንተርናሽል ያወጣበት 49 ሚሊየን ፓውንድ ሂሳብ በትክክል የሚመጥነው መሆኑ አጠራጣሪ ሲሆንባቸው መታየታቸው የተለመደ ሆኗል፡፡ ሆኖም ግን የማንቸስተር ሲቲው አሰልጣኝ ማኑኤል ፔሌግሪኒ ስተርሊንግን የገዙበት የዋጋ መጠን ትክክለኛ መሆኑ በአዲሱ ሲዝን ተጫዋቹ ለቡድናቸው በሚኖረው ቁልፍ ሚና በትክክል እንደሚጋገጥ እርግጠኛ ሆነዋል፡፡

‹‹ራሂም ስተርሊንግ በአሁኑ ወቅት በዓለም ፉትቦል ከሚገኙት እጅግ የተዋጣለት ብቃት ካላቸው የማጥቃት ላይ ያተኮረ ውጤታማ እንቅስቃሴ ካላቸው ምርጥ ፉትቦለሮች አንዱ ነው፡፡ ለዚህ ምንም አይነት ጥርጣሬ ስለሌለኝም ክለባችን በውድ ዋጋ እንዲገዛው ባደረግኩት ውሳኔዬ ሙሉ ኃላፊነትን እንደምወስድለት ማረጋገጥ እወዳለሁ›› ያሉት ቺሊያዊው አሰልጣን በመቀጠልም ‹‹እርግጠኛ ሆኜ ለመናገር የምወደውም የማንቸስተር ሲቲ ደጋፊዎች በዚህ ተጨዋች አስገራሚ ብቃት ገና ከመጀመሪያ ግጥሚያው አንስቶ ሙሉ ለሙሉ ደስተኛ የሚሆኑበት መሆኑን ነው፡፡ የዝውውር ውሉ ከወዲሁ ሙሉ ለሙሉ ተፈፃሚ መሆን መቻሉም ከሌሎቹ የቡድናችን ተሰላፊዎች ጋር በመሆን በአውስትራሊያና ወደ ሩቅ ምስራቅ በመጓዝ የምናደርገውን የፕሪ ሲዝን ዝግጅት ጉዞ ላይ ተሳታፊ ለመሆን የሚረዳው ነው፡፡ ከዚህ አንፃር ስተርሊንግ ከቡድናችን የጨዋታ ስታይል ጋር በፍጥነት ለመዋሃድ እንደሚችል ምንም አይነት ጥርጣሬ የለኝም›› የሚል አስተያየታቸውን አክለዋል፡፡

ማንቸስተር ዩናይትድ አንሄል ዲ ማሪያን እንዲሁም ቼልሲ ፈርናንዶ ቶሬስን ከገዛባቸው ውሎች ቀጥሎ ማንቸስተር ሲቲ በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ውድድር ታሪክ ሶስተኛው ትልቅ ዋጋ የወጣበት ስተርሊንግ በበኩሉ ለአዲሱ ክለቡ ደጋፊዎች ባስተላለፈው መልዕክቱ ‹‹ማንቸስተር ሲቲን ወደ መሰለ ግዙፍ ስኳድ ወዳለው ክለብ የመጣሁት የትላልቅ ውድድሮች የዋንጫ ሽልማቶችን ለማግኘት ያለኝን ጉጉት ለማሳካት እንድችል የበኩሌን ትልቅ እገዛን ለማበርከት የምችልበት አስተማማኝ ብቃትን ለመላበስ ለመቻል ሙሉ ለሙሉ እርግጠኛ በመሆኔ ነው፡፡ ከዚህ አንፃር በዚህ ክለብ ቆይታዬ ተደናቂ ስኬት እንደሚኖረኝ ከወዲሁ ለማንቸስተር ሲቲ ደጋፊዎች ቃል ልገባላቸው እወዳለሁ›› ብሏል፡፡

የራሂም ስተርሊንግ ውጣ ውረድ የበዛበት የአንፊልድ ቆይታው ሲዳሰስ

በአሁኑ የዝውውር መስኮት በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ከተፈፀሙት ውሎች ውስጥ በአወዛጋቢነቱ ቅድሚያ የተሰጠው ራሂም ስተርሊንግ ለሊቨርፑል በበቂ ሁኔታ ጥቅም ሳይሰጥ ለማንቸስተር ሲቲ የፈረመበት መሆኑ ይታወቃል፡፡ ተጨዋቹ ሊቨርፑልን የመልቀቅ ሃሳብ እንዳለው ለመጀመሪያ ጊዜ ይፋ የሆነው አሰልጣኝ ብሬንዳን ሮጀርስ ማርች 20/2015 በሰጡት መግለጫ ስተርሊንግ ክለባቸው ያቀረበለት የሳምንት ደመወዝን ወደ 100 ሺ ፓውንድ ኮንትራት ውል ማራዘምን እንደማይቀበለው እንደነገራቸው ይፋዊ መግለጫ ከተሰጠ በኋላ ነው፡፡

ከዛ ወዲህ ባሉት ወራት ውስጥ ሮጀርስና ሌሎቹ ኃላፊዎች የስተርሊንግን ሃሳብ ለማስቀየር የተቻላቸውን ሁሉ ጥረት ቢያደርጉም የ20 ዓመቱ እንግሊዛዊው ኢንተርናሽል የከፍተኛ ደመወዝ ተከፋይ የመሆን ጉጉትን ለመቀልበስ ሳይችሉ በመቅረታቸው በክለባቸው ደጋፊዎች ትልቅ ተስፋ አሳድሮ የዘለቀው ቁልፍ ተጨዋችን በ49 ሚሊየን ፓውንድ ሂሳብ ለማንቸስተር ሲቲ ለመሸጥ ተገድደዋል፡፡ ባለፈው ሳምንት በይፋ በተፈረመው ውል ስተርሊንግ ለማንቸስተር ሲቲ ለመጫወት የተስማማው በአምስት ዓመታት ኮንትራት ውል ነው፡፡ በዛኑ ቆይታው ማንቸስተር ሲቲ 180 ሺ ፓውንድ የሳምንት ደመወዝ የሚከፍለውም ይሆናል፡፡

ይህንን እውነታን ከግንዛቤ በማስገባትም የፉትቦል ተንታኞች ስተርሊንግ ዕድሜው 15 ለመድፈን ሲቃረብ ኪው.ፒ.አርን በመልቀቅ ለሊቨርፑል ከፈረመ በኋላ በአንፊልድ የፉትቦል ህይወቱ ያጋጠመው አጠቃላዩ ሁኔታን ከዚህ በታች ባለው መልኩ መለስ ብለው ቃኝተውታል፡፡

 

ፌብርዋሪ 2010

ሊቨርፑል ራሂም ስተርሊንግን ከኪውፒአር ለመግዛት በተደረገው ጨረታ ከማንችስተር ዩናይትድ፣ ከማንቸስተር ሲቲ እና ከአርሰናል ጋር ያጋጠመውን ጨረታ በማሸነፍ ከ500 ሺ ፓውንድ ሂሳብ ገዝቶታል፡፡ በወቅቱ የዝውውር ስምምነት ውል ላይ ሊቨርፑል ተጨዋቹን መልሶ በሚሸጠው ወቅት ከሚያገኘው ሂሳብ 20 ፐርሰንቱን ለኪው.ፒ.አር ያካፍላል የሚለው አንቀጽ ተጠቅሶበታል፡፡

ፌብርዋሪ 2011

የሊቨርፑል ወጣት ቡድን የሳውዝ ኢንድ አቻውን 9ለ0 በሆነ ሰፊ ውጤት በረታበት የኤፍ.ኤ ዩዝ ካፕ ላይ ስተርሊንግ 5 ጎሎን በስሙ አስመዝግቧል፡፡

ማርች 2012

ዕድሜው 17 ዓመት ከ107 ቀናት በነበረበት ወቅት ስተርሊንግ ተቀይሮ በመግባት ሊቨርፑል ዊጋን አትሌቲክን 2ለ1 በረታበት ግጥሚያ ለመጀመሪያ ጊዜ ለዋናው ቡድን ተሰልፏል፡፡ ያንን ግጥሚያ ያደረገው በዛን ወቅት የሊቨርፑል አሰልጣን የነበሩት ኬኒ ዳግሊሽ ጨዋታው ሊጠናቀቅ ደቂቃዎች ብቻ ሲቀሩት በሆላንዳዊው ዲርክ ካይት ምትክ ቀይረውት አስገብተውት ነው፡፡

ኦክቶበር 2012

በአንፊልድ ሮድ በተደረገው ግጥሚያ ለሊቨርፑል የመጀመሪያው የነጥብ ጨዋታ ጎልን በስሙ ለማስመዝገብ ችሏል፡፡ ስተርሊንግ በጨዋታው 29ኛ ደቂቃ ላይ ከመረብ ያሳረፉት ጎሉ በመታገዝ የአሰልጣን ብሬንዳን ሮጀርስን ቡድን ሬዲንግን 1ለ0 ለማሸነፍ ችሏል፡፡

አፕሪል 2014

ለሊቨርፑል ዋናው ቡድን ለሙሉ ሲዝን ባደረጉት ግጥሚያዎች በአብዛኛዎቹ ጨዋታዎች ላይ በመሰለፍ የአሰልጣኝ ብሬንዳን ሮጀርስ ቡድን ጠንካራ የፕሪሚየር ሊግ ሻምፒዮንነት ፉክክርን እንዲያደርግ ረድቶታል፡፡ በተለይም በአፕሪል 2014 ስተርሊንግ ለሊቨርፑል ድል መገኘት ከፍተኛ ወሳኝነት ያላቸው ሶስት ጎሎችን ለማስቆጠር ችሏል፡፡ የስተርሊንግ ሶስት ወሳኝ ጎሎች ከመረብ ያረፉት ሊቨርል ማንቸስተር ሲቲና ኖርዊችን 3ለ2 በሆነ ተመሳሳይ ውጤት በረታባቸው የፕሪሚየር ሊግ ግጥሚያዎች ላይ ነው፡፡

ጁን 2014

ለእንግሊዝ ዋናው ቡድን ለመጀመሪያ ጊዜ በተሰለፈበት የ2014 የዓለም ዋንጫ ውድድር በሶቱም የአገሩ የምድብ ማጣሪያ ግጥሚያዎች ላይ በመደበኛ ቋሚ ተሰላፊነት በመጫወት ለወደፊቱ ትልቅ ተስፋ የሚጣልበትን ውጤታማ እንቅስቃሴን ለማበርከት ችሏል፡፡ ሆኖም ግን የእንግሊዝ ብሔራዊ ቡድን ከምድብ ማጣሪያው ውጭ ከመሆን አደጋ ሳያተርፈው ቀርቷል፡፡

ኦገስት 2014

ለእንግሊዝ ዋናው ቡድን ለመጀመሪያ ጊዜ በተሰለፈበት የ2014 የዓለም ዋንጫ ውድድር በሶስቱም የአገሩ የምድብ ማጣሪያ ግጥሚያዎች ላይ በመደበኛ ቋሚ ተሰላፊነት በመጫወት ለወደፊቱ ትልቅ ተስፋ የሚጣልበትን ውጤታማ እንቅስቃሴን ለማበርከት ችሏል፡፡ ሆኖም ግን የእንግሊዝ ብሔራዊ ቡድን ከምድብ ማጣሪያው ውጭ ከመሆን አደጋ ሳያተርፈው ቀርቷል፡፡

ኦገስት 2014

ሰርተርሊንግ የ2014/15 ሲዝንን የከፈተው በመጀመሪያዎቹ ሶት የፕሪሚየር ሊግ ግጥሚያዎቹ ሁለት ወሳኝ ጎሎችን በማስቆጠር የታጀበ ውጤታማ ፉትቦልን በማበርከት ነው፡፡ ጎሎቹን ከመረብ ያሳረፈው ሊቨርፑል ሳውዝ አምፕተንን በአንፊልድ 2ለ1 እና ቶተንሃምን በኋይት ኸርትሌን 3ለ0 በረታበት ጨዋታዎች ላይ ነው፡፡

ኦክቶበር 2014

የውድድር ዘመኑን በእያንዳንዱ የሊቨርፑል ግጥሚያዎች ላይ በመሰለፍ ከጀመረ በኋላ በእንግሊዝ ብሔራዊ ቡድን ሁለት ግጥሚያዎች ለማጠናቀቅ የሚያስችለው ትንፋሽ እንደማይኖረው ለአሰልጣን ሮይ ሆጅሰን ነግሯቸዋል፡፡ በዚህም ሆጅሰን ከሳንማሪኖ ጋር በተደረገው ግጥሚያ ለ45 ደቂቃዎች እንዲሁም ኢስቶኒያን ሲገጥሙ በመጨረሻዎቹ 30 ደቂቃዎች ውስጥ ተጠቅመውበታል፡፡

ጃንዋሪ 2015

በውድድር ዘመኑ አጋማሽ ላይ የሊቨርፑሉ አሰልጣኝ ብሬንዳን ሮጀርስ ብዛት ያላቸውን ግጥሚያዎች ማድረጉን ከግንዛቤ በማስገባት የጥቂት ቀናቶች የእረፍት ጊዜውን ወደ ትውልድ አገሩ ጃማይካ በመሄድ ባሳለፈበት ወቅት የሊቨርፑል ሁለት ወሳኝ ግጥሚያዎች አምልጠውበታል፡፡

አፕሪል 2015

ስተርሊንግ ከቢቢሲ ጋር ባደረገው ቃለ ምልልስ ከሊቨርፑል የቀረበለት የተጨማሪ ዓመታት ኮንትራት ማራዘሚያ ውልን ለመቀበል መወሰኑን በይፋ አረጋግጧል፡፡ ሊቨርፑልን ለመልቀቅ ያሰበው ከገንዘብ ጥቅም ጋር በተያያዘ አለመሆኑን መግለጫውን ሰጥቷል፡፡

ሜይ 2015

የስተርሊንግ ወኪል ተጨዋቹ ከሊቨርፑል በቀረበለት የኮንትራት ማራዘሚያ ውል ዙሪያ መነጋገርን ጨርሶ እንደማይፈልግ ማጋገጫውን ሰጥቷል፡፡

ጁን 2015 

ማንቸስተር ሲቲ ስተርሊንግን በ2ኛው ሙከራው በ40 ሚሊየን ፓውንድ ለመግዛት ያቀረበው ሂሳብ በሊቨርፑል ኃላፊዎች ውድቅ ሆኖበታል፡፡

ጁላይ 2015

ስተርሊንግ የሊቨርፑልን የፕሪ ሲዝን ዝግጅት ቢጀመርም ከቡድኑ ጋር ግን ለዝግጅት ወደ ሩቅ ምስራቅ ለመጓዝ ፈቃደኛ ሳይሆንለት ቀርቷል፡፡ በዛኑ ማግስት ማንቸስተር ሲቲ በሶስተኛው ጥሪው ባቀረበው 49 ሚሊየን ፓውንድ ሂብ በሊቨርፑል ኃላፊዎች ተቀባይነት አግኝቶለት ስተርሊንግን በእጁ አስገብቶታል፡፡

The post Sport: ራሂም ስተርሊንግ ‹‹በማንችስተር ሲቲ ስኬታማ እንደምሆን እርግጠኛ ነኝ›› appeared first on Zehabesha Amharic.

Viewing all 15006 articles
Browse latest View live