በጣና ሀይቅ የተከሰተው እንቦጭ አረም ከመቀነስ ይልቅ አሳሳቢ ደረጃ ላይ መድረሱ ተዘገበ፡፡ በረራ ጋዜጣ ዛሬ እንደዘገበው አረሙን ለማጥፋት የተለያዩ ጥናቶች ቀርበው ሙከራዎች ቢደረጉም እስካሁን ፍሬያማ ውጤት አልተገኘም፡፡ የጎንደርና የባህር ዳር ዩኒቨርስቲዎች ማጨጃ ማሽኖችን በመግዛት ለማስወገድ እንቅስቃሴ ቢያደርጉም ያመጡት ነገር የለም፡፡ እንደውም ባህር ዳር ዩኒቨርስቲ ለባዮሌጂካል ሙከራ ብሎ የወሰደው የእንቦጭ ናሙና አባይ ወንዝን ዕየወረረው እንደሚገኝ ተገልጿል፡፡ […]
↧