Quantcast
Channel: Ethiopian News | ዘ-ሐበሻ | Latest News Provider | News For All
Viewing all 15006 articles
Browse latest View live

በስደት የትዮጵያ መምህራን ማህበር አባላት አስተባባሪ ኮሚቴ (ኢመማ) የተሰጠ መግለጫ

↧

↧

አብርሀ ደስታ ከምሽቱ 12፡00 ሰዓት ላይ ፍርድ ቤት ቀረበ

$
0
0

Abrha Destaካሳለፍነው ማክሰኞ ሐምሌ 1 ቀን 2006 ዓ.ም ጀምሮ በመንግስት ታጣቂዎች በቁጥጥር ስር ውለው በማዕከላዊ በእስር ላይ የሚገኙት ወጣቱ ፖለቲከኛ ሀብታሙ አያሌው የአንድነት ፓርቲ ህዝብ ግንኙነት ሀላፊ፣ ወጣቱ ፖለቲከኛ ዳንኤል ሺበሺ የአንድነት ፓርቲ ድርጅት ጉዳይ ም/ሀላፊ ወጣቱ መምህርና ፖለቲከኛ አብርሃ ደስታ የአረና ፓርቲ አመራር በትላንትው ዕለት ፍርድ ቤት ይቀርባሉ ተብሎ ቢጠበቅም ከምሽቱ 12፡16 ላይ የአረና ፓርቲ ህዝብ ግንኙነት ሀላፊ አብርሃ ደስታ ብቻውን በ3 ፌደራል ፖሊሶች ታጅቦ ፍርድ ቤት ቀርቧል፡፡ ማንም ወደ ፍርድ ቤቱ እንዳይገባ በፀጥታ ሀይሎችና ሲቪል በለበሱ የደህንነት ሀይሎች በመከልከሉ ምክንያት ስለቀረበበት ክስ ለማወቅ ያደረግነው ጥረት ሊሳካልን አልቻለም፡፡ በወጣቱ ፖለቲከኛ አብርሃ ደስታ ፊት ላይ ይታይ የነበረው ጉስቁልና ከፍተኛ የሀይል እርምጃዎች ሳይወሰድበት እንዳልቀረ አመላካች ነበር፡፡ ይህንን ዜና እስካጠናቀርንበት ጊዜ ድረስ የአንድነትና ሰማያዊ ፓርቲ አመራሮች ፍርድ ቤት አልቀረቡም፡፡

Millions of voices for freedom – UDJ
↧

ህገ መንግስቱን የጣሰው ማዕከላዊ ተከሰሰ

$
0
0

የአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮች የሆኑት አቶ ሐብታሙ አያሌውና አቶ ዳንኤል ሺበሺን ባሳለፍነው ማክሰኞ በቁጥጥር ስር ያዋላቸው የማዕከላዊ ወንጀል ምርመራ ፖለቲከኞቹን በህገ መንግስቱ በተጠቀሰው መሰረት እጃቸውን በያዘበት 48 ሰዓት ውስጥ ፍርድ ቤት ሊያቀርባቸው ባለመቻሉ ጠበቆቻቸው ክስ መመስረታቸው ታውቋል፡፡ ታሳሪዎቹን በማዕከላዊ የማግኘት መብታቸውን የተነፈጉት ጠበቃ ተማም አባቡልጉና ጠበቃ ገበየሁ ይርዳው በዛሬው ዕለት በአራዳ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት በመገኘት ማዕከላዊ የወንጀል ምርመራ ያሰራቸውን ሰዎች በፍርድ ቤት ትዕዛዝ እንዲያቀርባቸውና የሚገኙበትንና የተያዙበትን ምክንያት እንዲያስረዳ የክስ ፋይል ከፍተዋል፡፡

Millions of voices for freedom – UDJ
10494588_750671571658261_8784450188684809422_n

አቶ ዳንኤል ሺበሺ

habtamu ayalew

አቶ ሐብታሙ አያሌው

↧

ከአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) እና ከመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ) የተሰጠ ጋዜጣዊ መግለጫ

$
0
0

ኢህአዴግ በምርጫ ዋዜማ የጀመረው እስር በአምባገነንነት መስመሩ ለመቀጠል የቆረጠ መሆኑን የሚያረጋግጥ ነው!!!

በፖለቲካ አመለካከታቸው እና እምነታቸው የታሰሩ ዜጎች ያለምንም ቅድመ ሁኔታ እንዲፈቱ በድጋሚ እንጠይቃለን!!

ሕወሓት/ኢህአዴግ  ለአለፉት 23 ዓመታትወደርየሌለው የዴሞክራሲያዊ መብት ገፈፋና የሰብአዊመብትረገጣበዜጎችላይሲፈጽምመቆየቱና አሁንም በዚያው የአፈናና እስር መንገድ መቀጠሉንዓለምየሚያውቀውእውነታነው፡፡በአሁኑወቅት በተለይም በሚቀጥለው ዓመት የሚካሔደውን ሀገራቀፍ ምርጫ ተከትሎና ሁለቱ ፓርቲዎች የጀመሩትን የውህድት ጉዞ ለማደናቀፍ ባለመ መልኩ የሰብአዊመብትረገጣና ድፍጠጣ እንዲሁም ማሰሩና ማዋከቡበእጅጉተባብሶወደመንግሥታዊሕገ ወጥነት  ጥቃትተቀይሯል፡፡ ዜጎችመንግሥትእንዳሰማራቸው በሚጠረጠሩየደህንነትኃይሎች ስርዓቱን በሃይል ለማስቀጠል በመቁረጥ ዜጎች ኃላፊነት በጎደለው መልኩ ያለፍርድቤትትእዛዝበጅምላመታሰራቸውን፣መደብደባቸውንናበስውርእስር ቤቶችተወርውረውደብዛቸውእንዲጠፋመደረጉ ቀጥሏል፡፡ እንደዚህ አይነቱ ሕገ ወጥነት  ደግሞ ምርጫ ሲቃረብና የፖለቲካ ፓርቲዎች መሰባሰብ ብሎም መዋሃድ ሲገለፅ ተጠናክሮ የሚቀጥል እንደሆነ ከዚህ በፊት ከነበሩ ተሞክሮዎች ለመረዳት ይቻላል፡፡

ሕወሓት/ኢህአዴግለባለፉት 23 ዓመታት ሲያደርገው እንደነበረው ሁሉ ምርጫ ሲደርስ አባሎቻችንን ከመደብደብና ከማሳደድ በተጨማሪም በምርጫው ዋዜማ በተለመደውና አሰልቺ ፍረጃው ተደግፎ አመራሮቻችንን ማሰር ጀምሯል፡፡ እስሩም በፓርቲ ከፍተኛ አመራሮች ላይ ያነጣጠረ ሲሆን ሰሞኑን ብቻ አንድነት የስራ አስፈፃሚ አባልና የህዝብ ግንኙነት ሃላፊ የሆኑትን አቶ ሀብታሙ አያሌውን፤ የምክር ቤት አባልና የድርጅት ጉዳይ ምክትል ሃላፊ አቶ ዳንኤል ሺበሺን፤ የአረና የህዝብ ግንኙነት ሃላፊ የሆነውን አቶ አብርሃ ደስታን እና የሰማያዊ ፓርቲ ም/ቤት ምክትል አፈ ጉባዔ የሆነውን አቶ የሽዋስ አሰፋን አስሯል፡፡ በተጨማሪም ሰብዓዊ መብታቸውን በመግፈፍ ከ48 ሰዓት በላይ ፍርድ ቤት ሳይቀርቡ ቀርተዋል፡፡ በጠበቃም ሆነ በወዳጅ ዘመዶቻቸው አይጎበኙም፡፡ በአካላቸውም ሆነ በስነ ልቦናቸው የደረሰባቸውን ጉዳት ማረጋገጥ አልተቻለም፡፡ ስለዚህ ሁለቱ ፓርቲዎች እንደዚህ አይነቱን ሃላፊነት የማይሰማውና የጭካኔ ተግባር ማውገዝ ብቻ ሳይሆን እስከመጨረሻው ፍፁም ሠላማዊ በሆነ መንገድ  አምርረን የምንታገለው መሆኑን እናረጋግጣለን፡፡

የሰሞኑ እስር እንደተለመደው የተቀነባበረ የስርዓቱ ድራማ ከመሆኑም በተጨማሪ የ2007ን ሀገራቀፍ ምርጫ በተለመደው ማሸማቀቅና ማወናበድ ለመውሰድ የተጀመረ የመጀመሪያ ርምጃ ነው ብለንም እናምናለን፡፡ የተቀነባበረ ድራማም በሚቆጣጠራቸው ስማቸው የህዝብ ተግባራቸው ግን የኢህአዴግ  የፓርቲ መገልገያ በሆኑ ሚዲያዎች ማቅረቡን እንደሚቀጥልም እናውቃለን፡፡ ይህ ሁሉ ግፍና ድራማ የሚከናወነው ከአፍ ባለፈ መተግበር ያልቻለውን ዴሞክራሲያዊ ስርዓት ለማስመሰያነት ለመጠቀምና የቀጣዩን ዓመት ምርጫ በለመደው ሁኔታ ከቻለ አስሮና አደናግሮ ካልተቻለ ጉልበቱን ተጠቅሞ ለመጠቅለል ነው፡፡

አንድነትና መኢአድ  አባላትንና አመራሮቻችንን በተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች  በማሰቃየትናበማሸማቀቅ፣በመደብደብየአካልማጉደልጉዳትበማድረስየሚያደርገውንአስነዋሪተግባርእያወገዘንበግፍ የተታሰሩት አቶ ሀብታሙ አያሌው፤ አቶ ዳንኤል ሺበሺ፤ አቶ አብርሃ ደስታ እና አቶ የሺዋስ አሰፋ እንዲሁም በስርዓቱ በፖለቲካ አመለካከታቸውና እምነታቸው ብቻ ለእስር የተዳረጉ ፖለቲከኞች፤ ጋዜጠኞችና ብሎገሮች ያለምንም ቅድመ ሁኔታ እንዲፈቱ እናሳስባለን፡፡

 

በተጨማሪም በተቃውሞ ጎራ የተሰለፉ ፓርቲዎችም ይህን ህገ ወጥ እስር በማውገዝ እንዲሁም ኢ-ፍትሀዊ ምርጫ ለማካሄድ የሚደረገውን ሩጫ በመቃወም እጅ ለእጅ ተያይዘን እንድንቆም እየጠየቅን ይህንን ህገ-ወጥነት በህዝባዊና ሠላማዊ  ንቅናቄ፣ በነፃና ፍትሓዊ ምርጫ መለወጥ  እንዲቻል በጋራ እንድንሰራ ሀገራዊና ወቅታዊ ጥሪ እናቀርባለባለን፡፡ የሲቪክ ተቀቋማት፤ ነፃው ሚዲያና የሰብዓዊ መብት ተቆርቋሪ  ድርጅቶችም በኢትዮጵያ ሕዝብ ላይ እየተፈፀመ ያለውን መንግስታዊ ግፍና በደል በዓለማቀፍ ደረጃ በማጋለጥ ግዴታችሁን እንድትወጡ እንጠይቃለን፡፡  ገዢው ፓርቲ የሚከተለው የጉልበት ርምጃ ሀገሪቱን የሚያጠፋና ለትውልድ ጥላቻ የሚያወርስ  በመሆኑ ከዚህ ድርጊቱ እንዲቆጠብ እንጠይቃለን፡፡   የኢትዮጵያ ህዝብም ስለሰብዓዊ መብት መከበርና ዴሞክራሲ መረጋገጥ እየተደረገ ያለውን ትግል በመደገፍ የአምባገነኖችን ውድቀት እንዲያፋጥን ሀገር አቀፍ ጥሪያችንን እናቀርባለን፡፡

 

ድል ለሠፊው ህዝብ!!!

  አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) እና   

የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ)  

    ሐምሌ 3 ቀን 2006 ዓ.ም

                             አዲስ አበባ

udJ&AEUP

 

 

 

↧

ትግሉ የጥቂቶች ሳይሆን የሚሊዮኖች ሆኗል

$
0
0

ANAASO

በአገር ዉስጥም ሆነ ከአገር ዉጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን ጉጉትና ምኞት ፣ ልጆችዋ ከርሷ የሚሰደዱባት ሳይሆን የተሰደዱት ተመልሰው ለሌሎች መጠጊያ የምትሆን፣ የሕግ የበላይነት የሰፈነባት፣ የሰብአዊ መብቶች የሚከበሩባት፣ ዘር፣ ኃይማኖት፣ ጾታና መደብ ሳይባል ለሁሉም እኩል የሆነች፣ አንዲት ዲሞክራሲያዊት ኢትዮጵያን ማየት ነው።ነገር ግን፣  ከጊዜ ወደ ጊዜ በአገዛዙ እያየን ያለነው፣  ልብን የሚያደማና የሚያቆስል ነው። በስድሳዎቹ ከነበረው የደርግ ስርዓት በባሰ፣ አገዛዙ ሕዝባችን ላይ የግፍ ቀንበር ጭኖ ፣ የጸረ-ሽብርተኝነት ሕግ በሚል ሰበብ ሰላማዊ ዜጎችን እያሸበረ ነው።

 

የአንድነት ፓርቲ፣ የሚሊዮኖች ድምጽ ንቅናቄ በሚል መርህ፣ በተለያዩ የአገራችን ክፍሎች፣ ሕዝቡ ለመብቱና ለነጻነቱ እንዲቆም በመቀስቀስ፣ በዞን እና በወረዳ ደረጃ ድርጅታዊ ሥራ በመስራት፣ በርካታ ሰላማዊ ሰልፎችን እና ሕዝባዊ ስብሰባዎችን እያደረገ እንዳለ ይታወቃል። በቅርቡም ከመኢአድ ጋር የቅድመ ዉህደት ስምምነትን በመፈረም የዴሞክራቲክ ካምፑን በአንድ ላይ ለማሰባሰብ ይቻል ዘንድ፣ ትልቅ ሥራ ተሰርቷል።  እነዚህ አገረ ሰፊ እንቅስቃሴዎች፣ አገዛዙን አስደግጠውታል፣ አሸብረውታልም። ሥር እየሰደደ በመጣዉ ሰላማዊ እንቅስቃሴ፣  ከጊዜ ወደ ጊዜ ድምጹን እያሰማ የመጣዉን የሕዝብ ጥያቄ፣ በአክብሮት ከመመለስ ይልቅ፣ አገዛዙ ከሕዝብ ጋር መላተምን መርጧል። በሕዝብ ዘንድ ከበሬታና ተወዳጅኘት ያላቸውን፣  በሰላማዊነታቸውና በአገር ወዳድነታቸው የሚታወቁትን ወጣት የፖለቲካ ፓርቲ መሪዎችን፣ ወጣት ጋዜጠኞችን እና ብሎገሮች፣ የዲሞክራሲ አክቲቪስቶችን በማሰርና በማስፈራራት ፣ ለነጻነት የሚደረገዉን እንቅስቅሴ ለመግታት ብሎም የሕዝቡን ድምጽ ለማፈን ደፋ ቀና እያለ ነው።

 

በቅርቡ የአንድነት ፓርቲ የሕዝብ ግንኙነት ክፍል ሃላፊ፣ የሚሊዮኖች ድምጽ ግብረ ኃይል፣ የመኢአድና አንድነትየውህደት ኮሚቴ ሰብሳቢአቶ ሃብታሙ አያሌው፣ የአንድነት የድርጅት ጉዳይ ም/ሰብሳቢ አቶ ዳንኤል ሺበሺ፣ የሰማያዊ ፓርቲ የምክር ቤት ም/ሰብሳቢ አቶ የሺዋስ አሰፋ ፣ የአረና ፓርቲ አመራር አባልና ታዋቂ ብሎገር አቶ አብርሃ ደስታእና ወገኖችን ህገ ወጥ በሆነ መንገድ አፍኖ እስርቤት ጥሎ ማሰቃየቱን አገዛዙ በሰፊው መያያዙ በጣም አሳዝኖናል። አስቆጥቶናልም። የተቀናጀ ህገወጥ ድርጊቶችን የምንኮንነዉና የምናወግዘው ሲሆን፣  አገዛዙም በሕዝቡ ላይ ጦርነት ማወጁን በገሃድ የሚያመላክት እንደሆነ ለማየት ችለናል።

 

በአሁኑ ጊዜ የሕዝቡ ስነልቦና ተቀይሯል። ኢትዮጵያዉያን ግፍን  ለመሸከም የሚችሉበት ትከሻ የላቸውም። ጥቂት ወጣት የሰላማዊ የፖለቲካ መሪዎችን በማሰር፣  ሕዝቡን አስፈራርቶና መብቱን ረግጦ የመግዛት ዘመን አልፏል። ትግሉ የጥቂቶች ሳይሆን የሚሊዮኖች ሆኗል። በአገር ውስጥና ከአገር ዉጭ ሕዝባዊና ሰላማዊ የእምቢተኝነት ዘመቻው ይጧጧፋል። አገዛዙ በያዘው ብረትና በፈረንጆች ድጋፍ ይመካሉ። እኛ ግን በዉስጣችን ባለው ኢትዮጵያዊ ወኔ፣ በገዛ  ክንዳችን እና በፈጣሪ ረድኤት እንመካለን። አገዛዙ ጥላቻን እና ጭካኔን፣ ዘረኝነትን እና መከፋፈልን  ይሰብካል። እኛ ግን ፍቅርን እና መቻቻልን፣ አንድነትን እና ኢትዮጵያዊነትን እንሰብካለን።

 

በርግጥ የታሰሩ ወጣት የፖለቲካ መሪዎች ወደ ወህኒ መዉረድ ሁላችንንም ያሳዘነና ያስቆጣ ቢሆንም ታሳሪዎቹ ግን ፣ እንደ ክብር ነው የሚያዩት። የነርሱን መፈታት እና  ለነርሱም አጋርነታችንን ማሳየት ከፈለግን፣ ማድረግ የሚኖርብን ፣ ከዝምታ ወጥተን፣ የፍርሃትን ካባ አዉልቀን፣  ከሚሊዮኖች አንዱ መሆን ነው።  ቆመን፣  ተዋርደን፣ ፈርተን እና ተሸማቀን ከመኖር፣ የሕሊና  ነጻነት አግኝተን በአካል መታሰር ይሻለናልና።

 

በአገር ቤት ያሉ የፖለቲካ መሪዎች ያላቸውን ቁርጠኝነት በዚህ አጋጣሚ እያደነቅን፣  ከነርሱ ጋር እጅ ለእጅ በመያያዝ ከመቼዉም ጊዜ በላይ የሰላም ትግሉን እንደምንደግፍ ለማረጋገጥ እንወዳለን። ሕወሃት/ኢሕአዴግ ከሽብር ድርጊቶቹ በአስቸኳይ ተቆጥቦ፣  አራቱ ወጣቶችን ጨምሮ የታሰሩ የሕሊና እስረኞችን በሙሉ በአስቸኳይ እንዲፈታ፣  የሕዝብን ጥያቄ ለራሱ ሲል እንዲያከብር እናስገነዝባለን። አገር በዱላና በጡንቻ አትገነባም። አገር የምትገነባው በፍቅር፣በመቻቻልና በመግባባት ነው። የአገዛዙ መሪዎች ልቦናቸውን ለፍቅር ያስገዙ እንላለን። እምቢ ካሉ፣ ካከረሩ ግን ታሪክ እንደሚያስተምረው አወዳደቃቸው እጅግ ታላቅ  እና አስከፊ እንደሚሆን ልናስጠነቅቃቸው እንወዳለን።

 

ኢትዮጵያዉያን ከተባበርን፣ ሁላችንም የድርሻችንን ለማበርከት ከተነሳን፣ ከሚሊዮኖች አንዱ ከሆንን፣ አገዛዙ ፈለገም አልፈለገም የታሰሩ ወገኖቻችን ይፈታሉ። የተሰደዱ ወደ አገራቸው ይመለሳሉ። የአገራችንን ትንሳኤ እናውጃለን።

 

 

የሰላም ትግሉ ተቀናጅቶና ተጠናክሮ ይቀጥላል!!!

 

የሰሜን አሜሪካ የአንድነት ድጋፍ ማህበር

 

↧
↧

ሶስተኛዉ የረመዳን የጁመዓ ተቃዉሞ ተደረገ

$
0
0
“ለከፈልነዉ መስዋእትነት አቻ ዉጤት እናመጣለን!” በሚል ጽኑ መንፈስ ኢትዮጵያዉያን ሙስሊሞች ዛሬም በተለያዩ ከተሞች ታላላቅ ሰላማዊ ሰልፎችን አድርገዋል። ይህ በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ሰዎች የተሳተፉበት ሰልፍ በተሳካ መልኩ የተጠናቀቀ መሆኑን ሰላማዊዉን ንቅናቄ የሚመራዉ ድምጻችን ይሰማ አስታዉቋል። በባለፈዉ ሳምንት በተደረገዉ ተቃዉሞ እስከ ሰላሳ የሚደርሱ የሰልፉ ተሳታፊዎች ተይዘዉ መታሰራቸዉን፤ ብሎም ፍርድ ቤት በአዉቶቢስ ተጭነዉ መቅረባቸዉን ለማወቅ ተችሏል። ህገ መንግስታዊ መብታችን እስኪከበር ድረስ እስር፣ግድያ፣መገረፍ፣መደብደብ እና መሰደድ ትግላችንን አይገታዉም፤እስከ ድል ደጃፎች ድረስ በጽናት መትመማችንን እንቀጥላለን ይላሉ ኢትዮጵያዉያን ሙስሊሞች።

‹ግፉ እንዲያበቃ የ1 ብር ሰደቃ›› በሚል መሪቃል የተካሄደው የዛሬ ጁሙዓ ሐምሌ 4/2006 የሰደቃ እና የዝምታ ተቃውሞ 
2
4 5 6 3 1
↧

ዛሬ ሐምሌ 5 ቀን 2006 ዓ.ም የወያኔን ጸረ-አገርና ሕዝብ ድርጊት በማወገዝ በሚኒሶታ ሕዝባዊ ተቃውሞ ሰልፍ ተደረገ።

$
0
0

የኢትዮጵያና የሕዝቦችዋ ደመኛ ጠላት የሆነው የወያኔ መንግሥት ሥልጣን ከወጣበት ከ1983 ዓም ጀምሮ በአገሪቱ ውስጥ ለነፃነት ፣ ለእኩልነት ፣ ለዲሞክራሲያው ሥርዓት የሚታገሉትን ከሕዝብ ልጆች በመግዸል ፣ በማሳር፣ ሰውሮ በማጥፋት፣በማሳቃየትና  መብታቸውን በመግፈፍ በጠመንጃ ኃይል በሥልጣን ላይ ተቆናጦ ይገኛል። ከዚህ በፊት ከሱዳን ፣ ከጅቡቲ ከኬንያ፣ ከሶማሌላንድ  መንግሥታት ጋር በማበር ኢትዮጵያውያንን አፍኖ በመውሰድ ለግድያና ለአስር ዳርጓቸዋል። ከሰሞኑ ደግሞ ከየመን መንግሥት ጋር  በመተባበር የግንቦት 7 ዋና ጻሐፍ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌን ከሰናዓ አይሮፕላን ጣቢያ ወደ ኤርትራ ለመሄድ ትራንዚት በሚያደርጉበት  ወቅት አፍኖ በመውሰድ ማሳሩን እንዲሁም የየመንን የኣለም አቀፍ ድንጋጌ የጠሳውን ሕገወጥ ድርጊትና በኢትዮጵያ የውስጥ ጉዳይ  ጣልቃ መግባቷን በመቃወም በሚኒሶታ ከፍተኛ ሕዝባዊ ተቃውሞ ስልፍ በሚኒሶታ ጠቅላይ ግዛት አስተዳደሪ ጽ/ቤት ፊት  ተካሄዷል። ሰልፈኛው በወክሎቻቸው አማካይነት ለአስተዳደሪው የተጸፈውን ደብዳቤ አቅርበዋል። በኢትዮጵያ ውስጥ የወያኔ  መንግሥት የሚፈጽመውን የሰብአዊ መብት ረገጠና ሌሎች ወንጀሎች በዝርዝር አስረድተዋል።

ሰልፈኛው ከ10፡00AM- 12:30 PM ድረስ ለአስተዳደሪው ጽ/ቤት ሰራተኞና በአካባቢው ቆመው ሰልፉን ለሚመለከቱ አሜሪካውያን  የሰልፉን ምክንያት በማስረዳት ከአሜሪካ ሕዝብ በሚሰባሰብ ገንዘብ በኢትዮጵያ ውስጥ ሕዝብ እየበደለ የሚገኛውን አምባገነን  መንግሥት መርዳት እንዲያቆም አሳስበዋል። ሰልፈኛው ግርማ ሞገሱ በሚያስፈራው የኢትዮጵያ ሰንዳቅዓላማ ተውቦ ብዙ  መፍክሮችንና ዜማዎችን በማዜም ወደ አስተዳደሪው ጽ/ቤት ደረሰ። ተይዘው ከነበሩት መፈክሮች ጥቂቶቹ የሚከተሉት ነበሩ፡-

 

ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር !!!
 ወያኔ የሕዝብ ጠላት ይወድማል!!
 የኢትዮጵያ ሕዝብ ያሸንፋል!!
 የዲሞክራሲ መብት ይከበር!!
 ዘረኝነት ይወገድ!!
 ሕዝብ ማፈናቀል ይቁም!!
 ወያኔ ገዳይ ነው!!
 ለትግል ቆርጠን እንነሳ!!
 የሕሊና እስረኞች በሙሉ ይፈቱ!!
 የኢትዮጵያን መሬት ለሱዳን መሰጠቱን በጥብቅ እንቃወማለን!!
 በቅርቡ በኦሮሞ ወገኖቻችን ላይ የተፈጸመውን ግድያ በጥብቅ እናወግዛለን!!
 Free Andargachew Tsige!
 Free Eskender Nega!
 Free Tsegaye Debteraw!
 Free All Political Prisoners in Ethiopia!
 Free Rhiot Alemu!
 Free Aberash Berta
 Free Muslim Peace Committee Leaders!!
 No Democracy!
 US stop helping the brutal regime in Ethiopia

 

ከዚያም ሰልፈኛው በመሰብሰብ የወያኔን የክክፍል ሴራ መቋቋም እንደሚያስፈልግ፣ ለዚህም መደራጀት እንደሚያስፈልግ ፣ ተደራጅተው የሚገኙ ድርጅቶችን መርዳት እንደሚያስፈልግ ፣ በወያኔዎች የንግድና ሌሎች ተቋማት ላይ እቀባ ማድረግ እንደሚያፈልግ  ፣ ወደፊት ለሚደረጉት ሁሉም ዓይነት እንቅስቃሴዎች አስቸኳይ መልስ በመስጣት የሥራ ግዴታዎችን መውጣትን በሚመለከት  ተነጋግሮ ከስምምነት ላይ በመድረስ ሰልፉ በሰላም ተጠናቋል። የሚኒሶታ ግብረኃይል( Task Force in Minnesota

IMG_0406[1]   IMG_0405[1]   IMG_0411[1]   IMG_0410[1] 
  IMG_0412[1]

↧

ቴዲ አፍሮ ሚኒሶታ ገባ –ዛሬ ቅዳሜ ምሽት በሚኒያፖሊስ የሚያደርገው ኮንሰርት በጉጉት ይጠበቃል

$
0
0

(ዘ-ሐበሻ) የኢትዮጵያ ሙዚቃ አብዮተኛ ተብሎ በበርካቶች አድናቆትን የተቸረው ቴዲ አፍሮ ዛሬ ቅዳሜ ጁላይ 12 በሚኒያፖሊስ ለሚያደርገው ኮንሰርት ሚኒሶታ ገባ። ድምፃዊው ከአንድ ሰዓት በላይ በዘገየው በረራው ሚኒሶታ ሲደርስ በርከት ያሉ አድናቂዎቹ ባንዲራ ይዘው በመቀበል ያላቸውን ፍቅር ገልጸውለታል።
teddy afro arrived minnesota
ቴዲ አፍሮ በሚኒያፖሊስ-ሴንት ፖል ኤርፖርት እንደደረሰ በዘ-ሐበሻ አማካኝነት በተደረገለት አጭር ቃለምልልስ ዛሬ በሚኒያፖሊስ የሚያሳየውን ኮንሰርት በጉጉት እንደሚጠብቀው ገልጾ “በፍቅር እና በሰላም ሚኒሶታ ደርሰናል፤ የፍቅርና የሰላም ኮንሰርታችንን እናደርጋለን” ብሏል። በሚሚሶታ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን የቴዲ አፍሮን መምጣት በጉጉት ሲጠባበቁት የነበረ ሲሆን በከተማዋ በሚገኘው ራስ ሬስቶራንት የራት ግብዣ ተደርጎለታል። በራት ግብዣው ወቅትም የቴዲ አፍቃሪዎች ፎቶ ግራፍ አብረው በመነሳት ድምፃዊውን “እንኳን በሰላም ወደ ሚኒሶታ መጣህ፤ የነገውን ዝግጅትህን በጉጉት እንጠብቃለን” ብለዋል።

በሚኒሶታ የሚደረገውን ይህን “የፍቅር ጉዞ” ኮንሰርት በተመለከተ አንዳንድ ሃገር ወዳድ መስለው ከበስተጀርባ ሌላ ዓላማ ያላቸው ድረገጾች አንዳንዶች ሊያውኩት ይችላሉ በሚል እያወሩ ቢሆንም ከሚኒያፖሊስ ፖሊስ እና ከሚኒያፖሊስ ከንቲባ ቢሮ ዘ-ሐበሻ ባገኘችው መረጃ መሠረት የቴዲ አፍሮ ኮንሰርት በሰላም ተጀምሮ በሰላም እንደሚጠናቀቅ ነው። እንደ ፖሊስ ገለጻ በሚኒሶታ ነዋሪ ነን ያሉና የኦሮሞ ማህበረሰብ ተወካዮች ነን ያሉ 5 ሰዎች ለፖሊሱና ለከንቲባው ጽህፈት ቤት ኮንሰርቱ እንዲሰረዝ ጥያቄ አቅርበው ነበር። ሆኖም ግን ይህ ሳይሳካ ቀርቷል። በተለይም ሚኒያፖሊስ በኦል ስታር ጨዋታዎች ከሌላ ስቴት በመጡ እንግዶች የተነሳ በከፍተኛ ጥበቃ ሥር ያለች ሲሆን የሚኒያፖሊስ ፖሊስም አስፈላጊውን ጥበቃ ለዚህ ኮንሰርት እንደሚያደርግ አስታውቋል።

ቴዲ አፍሮን “የፍቅር ጉዞ” ኮንሰርት ለመታደም ከሚኒሶታና አጎራባች የአሜሪካና የካናዳ ከተሞች በርካታ ወገኖች የገቡ ሲሆን ትኬቶችም በተለያዩ የኢትዮጵያውያን መደብሮች በመሸጥ ላይ ናቸው። ቅድሚያ ከሱቆች ለሚገዙ ዋጋው $37 ሲሆን በር ላይ $42 ነው። ከቴዲ አፍሮ ማናጀር አቶ ዘካሪያስ ጌታቸው ባገኘነው መረጃም የቴዲ ኮንሰርት በጊዜ ስለሚጀመር በሩ ከምሽቱ 9 ሰዓት ጀምሮ እንደሚከፈት አስታውቀዋል። ሁለት አዳዲስ ነጠላ ዜማዎቹንም በሚኒያፖሊሱ ኮንሰርት እንደሚያቀርባቸው ገልጸዋል።

የቴዲ ኮንሰርት በዳውንታውን ሚኒያፖሊስ Mill City Nights: 111 5th St N, Minneapolis, MN 55403, ይደረጋል። ለበለጠ መረጃ በ 651 955 6091 ወይም 612 226 8326 ይደውሉ።

↧

Health: ቃር እያሰቃየኝ ነው፣ መፍትሄውን ንገሩኝ

$
0
0

እንዴት ናችሁ? እኔ ከሰሞኑ ከሚያሰቃየኝ ቃር ውጪ ደህና ነኝ፡፡ ይህ ነው የሚባል የጨጓራ ችግር እስካሁን የለብኝም፡፡ አንዳንድ ጊዜ ከምበላው ነገር ይሆን ወይ? ብዬ ምግቦችን እየለዋወጥኩ መመገብ ጀምሬ ነበር፡፡ የሆነ ሆኖ ልቤን መፋቁ እና ቃር ሊተወኝ አልቻለም፡፡ እስቲ ስለቃር ምንነት እና መከላከያ ከዚያም ህክምና አማራጭ ካለ በዝርዝር አስረዱኝ፡፡
ask your doctor
ሰላም ውድ የአምዳችን ተከታታይ፤

ብዙዎቻችን ጋር አልፎ አልፎ መጠነኛ የልብ መቃጠል እና ምቾት ማጣት ሊከሰት መቻሉ የጤንነት እጦት አይደለም፡፡ ይሁንና እኛ በተመልዶ ‹ቃር› የምንለው ችግር በሳምንት ከሁለት ጊዜ በላይ ሲከሰት እና በቀላል መድሃኒቶች ማስታገስ ሳይቻል ሲቀር እንደ አሳሳቢ የጤና ችግር ይወሰዳል፡፡ በህክምናው ይህ የቃር እና የልብ ማቃጠል ‹ጋስትሮኢሶፋጂያል ሪፍለክስ ዲዚዝ› ተብሎ ይጠራል፡፡ ቃር የሚለው ቃል ሁኔታውን በሙሉ ባይገልፀውም ለመግባባት እንዲቀለን ቃር በሚለው መግለጫ እንቀጥላለን፡፡
ቃር በደረት አካባቢ የሚፈጠር እና የሚያቃጥል ስሜት ሲሆን ወደ አፍ ውስጥና ጉሮሮ አካባቢም ወደላይ ወጥቶ የሚሰማ ህመም ነው፡፡ ችግሩ በደረት ህመም፣ ለመዋጥ በመቸገር፣ ደረቅ ሳል፣ የጉሮሮ መጎርነን እና አንዳንድ ጊዜ የምግብ መጓጎጥ ስሜትን እና ምልክቶች በማሳየት ይገለፃል፡፡

ቃር የሚከሰተው በሆድ መቅረት ያለበት የምግብ መፍጫ አሲድ ወይም ቅባት ነክ ምግቦችን የሚፈጨው ሀሞት ከአንጀት ተነስቶ ሽቅብ ወደ ጉሮሮ ሲመጣ እና ማቃጠልን ሲፈጥር ነው፡፡ በተፈጥሮ ምግብ ስንውጥ የታችኛው የጉሮሮ መጨረሻ ላይ ያሉ ጡንቻዎች ፈታ ይሉና ምግብና ፈሳሽ ወደ ሆድ እንዲወርዱ መንገድ ይከፈታል፡፡ ምግብና ውሃው ወደ ሆድ ከገቡ በኋላ ጡንቻዎቹ ይዘጋሉ፡፡ ይሁንና ይህ የጡንቻዎቹ መክፈቻና መዝጊያ ከመጠን ባለፈ ሁኔታ ሲዳከም የሆድ ውስጥ አሲዶች ሆድን አልፈው ወደ ጉሮሮ ሽቅብ መምጣት ይጀምራሉ፡፡ የደረት እና ጉሮሮ አካባቢን ማቃጠል (ቃር) የሚፈጥሩትም እነዚሁ አሲዶች ናቸው፡፡

ማንም ሰው ቃር የሚታመም ቢሆንም በተለይ ወፍራም ሰዎች፣ ሲጋራ አጫሾች፣ ኸርኒያ ያለባቸው እና አስም ታማሚዎች የበለጠ ለቃር ተጋላጭ ሊሆኑ ይችላሉ፡፡ ቃር ለጊዜው ጉዳት የለሽ ጊዜያዊ እክል ቢመስልም ለረጅም ጊዜ መፍትሄ ሳይሰጠው ከቆየ ከበድ ያሉ ችግሮችን ሊያስከትል ይችላል፡፡ ከእነዚህም መካከል የጉሮሮ መጥበብ፣ የጉሮሮ ቁስለት መሰል መብላትና መጠጣትን የሚከለክሉ ችግሮች ተጠቃሽ ናቸው፡፡

ቃርን ለማስታገስ እና ጊዜያዊ የሆነ ፀረ አሲድ መድኃኒቶችን ከፋርማሲ በመግዛት መጠቀም ቢቻልም በቃሩ ምክንያት ቁስለት የተፈጠረበት ጉሮሮ ከሆነ መፍትሄ አይሆንም፡፡ አንቲ አሲድ መድኃኒቶችንም አለአግባብ ደጋግሞ መጠቀም የጎንዮሽ ጉዳቶች ስላሉት የባለሙያ ምክር የሚታከልበት እንዲሆን ያስፈልጋል፡፡ ሌሎች ጠንከር ያሉ መድኃኒቶችን በባለሙያ ካልታዘዙ በቀር መሞከርም ተገቢ አይደለም፡፡

ውድ ጠያቂያችን ቃሩ የቅርብ ጊዜ ችግርህ ስለሆነ ከበድ ያሉ ህክምናዎች የሚጠይቅህ አይመስለንም፡፡ መጀመሪያ ከምግብ መጠጥ እና አጠቃላይ አኗኗር ዘዬህ ጋር የተያያዙ ለውጦችን በማድረግ ችግሩን ለማሻሻል ብትሞክር ጥሩ ነው፡፡ በእነዚህ ለውጦች መካከል ክብደትህ በጤናማ ክልል ውስጥ እንደሆነ ማድረግ አንዱ ነው፡፡ ክብደት ሲበዛ ሆድን በመግፋት የሆድ አሲዶች ሽቅብ እንዲወጡ ያደርጋል፡፡ ወገብ አካባቢ የሚያጣብቁ ልብሶችን ማስወገድ፣ የማቃጠል ተፈጥሮ ያላቸውን እንደ የተጠበሱ ምግቦች፣ አልኮል መጠጥ እና ሽንኩርትን እንዲሁ መቀነስ ጠቃሚና ቃርን ማስወገጃ መንገዶች ናቸው፡፡ አንተ ራስህ ደግሞ ስትበላ ምቾት የሚነሱና የሚያቃጥሉህን ምግብና መጠጦች በደንብ ተከታትለህ ለያቸው እና በተቻለ መጠን አርቃቸው፡፡ ከመተኛትህ በፊት ቢያንስ ከሁለት ሰዓት በፊት መመገብ ሌሊት ላይ ቃር እንዳያስቸግር ያደርጋል፡፡ ስትተኛ ትራስህን ከፍ ማድረጉም በግራቪቲ እሳቤ አሲዱ እዚያው እታች እንዲቀር ይረዳል፡፡ ሲጋራ ማጨስና አልኮል መጠጥ አዘውታሪ ከሆንክ ከዚህም ብትርቅ መልካም ይመስለናል፡፡ የሚያጨናንቁ እና ውጥረት ውስጥ የሚከቱት ሁኔታዎችም አባባሽ የቃር ምክንያቶች የሚሆኑባቸው አጋጣሚዎችም ጥቂት አይደሉምና ይህንን አስብበት፡፡ የነገርንህ የመፍትሄ አቅጣጫዎችን ሞክራቸው፡፡ በአጭር ጊዜ መፍትሄ ካላገኘህ የውስጥ ደዌ ስፔሻሊስት ጋር ቀርበህ ምርመራና ህክምና ማድረግን እንመክራለን፤ ጤና ሁን!

↧
↧

አብረሃ ደስታ በትግራይ ጭለማ ውስጥ ያለ ፋኖስ

$
0
0

ከዳኛቸው ቢያድግልኝ

(አብርሃ ደስታ ከመቀሌ)

(አብርሃ ደስታ ከመቀሌ)

የእለት እለቱን የትግራይ ውሎ የሚያበስረን እውነትን ምርኩዝ አድርጎ አረናን ወግኖ የትግራይ ነፃ አውጪዎችን ነፃነት  ሳይሆን ሙልቅ ነው ያወጣችሁን ዲሞክራሲን ሳይሆን ሀፍረትን አከናነባችሁን ብሎ በመሞገቱ ከጠላት ተፈረጀ። ሴት ወይም ህፃን ልጅን እንደመከላከያ ከፊቱ አድርጎ ማምለጫ እንደሚፈልግ ዘራፊ የትግራይን ሕዝብ መሸሸጊያ ነው ያደረጋችሁት በወገኑ ማስጠላትና ያለናንተ ሕልውና የሌለው እንዲመስለው ማድረግን ነው የያዛችሁት። መበለጥ በቃን መሳርያ መሆን በቃን። በመቀሌ የገነባችሁት የአፓርታይድ መንደር የትግል መነሻችሁ የዝቅተኝነት ስሜት ግባችሁ ደግሞ ሁሉን ማግበስበስ መሆኑን ያሳያል በማለቱ ዳግማይ ጭፍጨፋ በሀውዜን ብሎ በመመስከሩ አሸበራቸውና በመጨረሻ ከለመዱት እስርቤት ጨመሩት።
አብርሃ አሁን ያለበትም አይታወቅምና የሚደርስበትን በደልና ጭካኔም አናውቀውም። ስለሁኔታውም የሚነግረን መኖሩን ገና አናውቅም።  ኢትዮጵያን የምንል፣ ነፃነትና ፍትህ ለሁሉም የምንል ግን ስለ አብርሃ ይጨንቀናል። ከመንደርና ከጎጥ በላይ በመሆን ስለ ኢትዮጵያ ማሰብ ደግሞ ይበልጥ ያስተሳስረናል የጠላቶቻችንን መንደርም ያሸብራል። የመከራው መብዛት፣ የስቃያችን መጨረሻ ማጣት ዋናው ምክንያት የጠላት አፈራረጃችንና መፍትሄ አፈላለጋችን የሩቁንና የቅርቡና ያላገናዘበ በመሆኑ ነጣጥለው ለሚመቱን ደካሞች እንዲመቻቸው ሆነ። ከዚህ አዙሪት በራሳችን እውቀትና አቅም በጊዜው መውጣት አልቻልንም።

አሁን ግን በግድ ወደ አንድ ጎራ እንድንመጣ እየተገፋን ነው ይህንንም አውቀን በደል ለደረሰባቸው ሁሉ በጋራ የምንጮህ ልንሆን ይገባል። ደቡብ ሱዳንን አስጨንቀን፣ ጅቡቲንና የኬንያ መንግስትን አውግዘን ቢሆን ኖሮ ምናልባት የመንም ባልተጨመረች ነበር። በደሎች ሁሉ እንዲያስቆጡን ወደ ውጤትም  እንድንሄድ አንድ መሆን ቢያቅተን የጋራ ስምምነት ያሻናል።  ከጊዳሚ እስከ ወሎንኮሚ ከመቀሌ እስከ ባሌ ከሀረር እስከ ጎንደር ኢትዮጵያን ያሉ ነፃነት እንሻለን ያሉ ሁሉ በየጉሮኖው  ተጥለዋል። ወያኔ ይቅር ብላ ያለፈቺው ይሁን ብላ የተወቺው አንዳችም ሰው የለም። አድፍጣ ለማደን የማትደክም አድና  በልታም ለመጥገብ ያልታደለች የእርጉማን ጥርቅም ነች። ቁጣችን ግን ወደ ወያኔ ብቻ ሳይሆን ወደራሳችንም ሊሆን ይገባል። ያሳበጥናት ያደለብናት አውሬነቷን እያደነቅን እስክትበላን እስር አስሯ የሄድን እኛው ነን። ጉልበት የሆናት መንገድም ያሳየናት እኛው ነን። እስኪበቃን አቅምሳናለችና በቃን ማለት ደግሞ የኛው ስራ ነው። አስጥሉን ብለን ብንጮህ የሚደርስልን የለምና
የኛ ነፃነት በኛው እጅ ናት።
እንደ አብርሃ ያሉ እውነትን የሚደፍሩ ኢትዮጵያዊነትን የሚያከብሩ እንዲበዙልን ምኞቴ ነው። አብርሃ ለእውነት እስከቆምክ፣ ለነፃነት እስከታገልክ ድረስ ከጎንህ የማይቆም የለምና ጽናትና መበረታታት እንዲኖርህ እመኛለሁ። በርካቶች ዝም ባሉበት ሰዐት ዘራቸውን ከሀገራቸው አስበልጠው ለጥቅማቸው በቆሙበት አስቸጋሪ ቦታና ሁኔታ ብቅ ያልክ ብርቱ ነህና ከትንሿ እስር ቤት ወደ ትልቁ መጥተህ ያንን እስር ቤት እንድናፈርሰው ምኞቴ ነው።
ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!

↧

የወረዛ ዕምል ታዛ። (ከሥርጉተ ሥላሴ)

$
0
0

10489የወረዛዕምል ታዛ

ቀፎ  የጠነዛ

ጠንባዛ – ጠምዛዛ፤

የዘመን አበሳ

ለዛዛ።

ስንት ፍሬ ሞልቶ

ምርጥ ዘር አግቶ

ተዘሎ ተረስቶ

በቅንቅን ተበልቶ

በጎሳ ተዛብቶ።

ሊቀ ሊቃውነቱ

የቀለም አባቱ

ነበራት ለትብቱ

የቁርጡ – የጥንቱ።

ጭዱ ተከምሮ

በተኩላ ተወሮ

አለቀሰ ዘመን

በባዶ ተዋቅሮ፤

በጭድም ተማሮ

በግለትም አሮ።

ታሪክ እንዲህ ያራል

ትውልድም ይመራል

በቀፎ በረሮ።

ታነባለች እናት

ደም ነፍስ ነግሦባት

ወናነት ቀሶባት

ውሉ ተንፍሶባት።

ክምርና – ድርድር

የጠፍነት – ግብር

የዕብለቱ ሰንበር

መጫወቻ አሰር

አሻንጉሊት ነስር

እስር!

መፍቻ።

  • ግለት ጠብቆ ሲነበብ – የወያኔ ሰፊው መርሁ የነፃነት ትግሉም ያልደረሰብት ምንአልባትም ሳያወቀው እዬተከተለው ያለው ሰፊው ፖሊሲ ነው። ሌላ ቀን ሰፋ ድርጌ እመጠበታለሁ። ሁለተኛው የግለት ላልቶ ሲነበብ በ እሳት መፋምን ለማመልከት ነው። የቃሉ አግባብ በሰምም በወርቅም ያስኬዳል ተጠቅምቤታለሁ።
  • ይመራል። ያስተዳድራል የሚለውን አይደለም ከዚህ ላይ ላማመልክት የፈለግሁት። ይጎመዝዛል የሚለውን ለማመልክት ነው። ትውልድ በደመነፍስ ሲማራ ያሸማቅቃል ውርዴትም ነው ለእኔ በግሌ። ሸምቀቆ ነገር።
  • ታዛ አዎን አቶ ሃይለማርያም ባዶ ቀፎ ናቸው ቀን የሚጠበቅላቸው ዛሬ ያሉ ቢመስላቸውም ወልቀው የሚቀሩ።  ከእንጉልቻቸው ሲባንኑ ይደርሱበታል። ለወያኔ ሃርነት ትግራይ እሳቸው ትቢያ ናቸው ተራግፈው የሚቀሩ። የቆዬ ሰው ያዬዋል። አሁንም መንፈሳቸውን የወያኔ ማንፌስቶ አብዝቶ ይጸዬፈዋል።  ግዱ ነው ያጠጋጋቸው። በዘነዘናቸው ነው እዬነገዱበት ያለው።
  • የወረዛ እርጥበት ያለው ግን እርጥበቱ እራሱን አሻግቶ ይፍራሳል ጠረኑ እምል ስለሚሆን ለትውልድ የሚቀፍ ይሆናል።

 

 

የእውነት አምላክ ፍርድ ይስጥ!

የበቀል አምላክም ቁጣ ይላክ – ለዕብለተኛው።

 

እግዚአብሄር ይስጥልኝ።

 

 

 

 

 

 

↧

‹የፈራሁት ነገር መጣ ድሆ ድሆ› (ብስራት ደረሰ)

$
0
0

ብስራት ደረሰ (ከአዲስ አበባ)

 

tplf

የፈሩት መድረሱ፣ የጠሉት መውረሱ ያለና የነበረም ነው፡፡ አንድን ነገር በሩቅ እያለ መዐዛው ሲያውድህ ወይም ቅርናትና ግማቱ ሲያጥወለውልህ በምናባዊ የስሜት ህዋስህ እየተሰማህ ስሜቱ ገና ላልተሰማቸው ልታስታውስና የማንቂያ ደወል ልታሰማ ትችል ይሆናል፡፡ ነገር ግን እንዳለመታደል ይሆንና ሰሚ ታጣለህ ወይም ከጉዳይ የሚጥፍህ አይኖርና እንዲሁ ደክመህ ትቀራለህ፡፡ የመጨረሻው መጨረሻ ሲመጣና በምናብህ የታየህ ነገር የሁሉንም ቤት መቆርቆር ሲጀምር ግን ቀዳሚው ዕይታህ እውነትና የማይቀርም መሆኑን አንተ ራስህም እንደሌላው እየተደመምክ ጊዜ ባለውሉን ታደንቃለህ፡፡ በአቶ አንዳርጋቸው ጽጌ በየመን መታፈንና ለትግሬው ነፃ አውጪ ወያኔ በቅጽበት ተላልፎ መሰጠት ሳቢያ ሰሞኑን እያስተዋልነው ያለነው ሀገራዊ ክስተት ይህን ነው የሚመስለው፡፡

በባህላዊ ዘፈኖቻችን በአንደኛው ውስጥ የመጀመሪያውን ስንኝ ለጊዜው ዘነጋሁት እንጂ በርዕሴ ላይ የጠቀስኩትን የመሰለ ተከታይ ስንኝ አለ፡፡ የሚፈራ ነገር ጊዜ ይፍጅ እንጂ መድረሱ የማይቀር መሆኑን ይጠቁማል፡፡ እኔም የፈራሁት፣ ብዙዎች ሩቅ ተመልካች ኢትዮጵያውያንም የፈሩት፣ ቀደም ካለ ዘመን ጀምሮ በአንዳንድ ኢትዮጵያውያን የትንቢት መዛግብት ውስጥም የተቀመጠውና በእጅጉ የተፈራው ነገር በቅርብ ሊፈጸም እንደሆነ ከዳር ዳርታው እየተረዳን በመሆናችን የፈራነው ነገር ድሆ ድሆ ስለመምጣቱ ቅንጣት መጠራጠር አይገባም፡፡ ለምንድንስ ነው የምንጠራጠረው? እንኳንስ ዘረኛው የትግሬ መንግሥት ከሆዳምነታቸውና ከጨካኝነታቸው በስተቀር በአንጻራዊ ሁኔታ ለሀገራቸው አንድነትና ለሕዝባቸው ደኅንነት ይተጉ የነበሩ የቀ.ኃ. ሥላሴንና የአፄ መንግሥቱ ኃ/ማርያምን የመሳሰሉ ኢትዮጵያውያን መንግሥታትስ ጊዜያቸውን ጠብቀው ወደታሪክ መዝገብነት ተለውጠው የለም እንዴ? ታዲያ የወያኔን ወረደ መቃብር መዳረስ ለምን እጠራጠራለሁ? የወያኔ የባሕርይ አባቶች ናዚው ሂትለር፣ ፋሽስቱ ሙሶሊኒ፣ አምባገነኖቹ መንግሥቱና ሞቡቱ፣ ኢድ አሚንና ጋዳፊ ወዘተ. ተራቸውን እየጠበቁ ወደማይቀረው ሞት ተጉዘዋል፡፡ የመለስ ዜናዊ ወያኔም የማይቀርለትን ዕዳ ሊወጣ ቁልቁለቱን በከፍተኛ ፍጥነት እየተንደረደረ ነው፡፡ ውሃ ውስጥ ገብቶ እየሰመጠ የሚገኝ ሟች ደግሞ የሚያድነው እየመሰለው ፊላና ሣር እንዲሁም የሚንሳፈፍ የወፍ ላባ ሳይቀር ይጨብጣል፡፡ ሞቱ ታሪካዊና የማይቀር የሆነው ወያኔ ደግሞ የሚድን እየመሰለው ይጨብጠውንና ይለቀውን አጥቶ በሚያሳዝን የኅልውና ሁኔታ ውስጥ ይገኛል – ጣረሞታዊ ኅልውናውን ኅልውና ካልነው፡፡

እርግጥ ነው – ወያኔ በመሞት ላይ ነው ስል የነጋበት ጅብ ብዙ ምናልባትም ሊጠገን የማይችል እጅግ ብዙ ጉዳት ማድረሱ እውነት እንደመሆኑ ወያኔም በዚህ የአመሻሽ ሰዓቱ – በዚህ የጣዕረ ሞት ቅጽበቱ ለግምት የሚከብድ ጠባሳ እንደሚያስከትል በተግባር እያየነው ነው፡፡ ስለዚህም ትግልን በተቻለ መጠን በጥንቃቄ ማድረጉ ብዙ ኪሣራ ውስጥ ላለመግባት ጠቃሚ ነውና ልብ ያለው ልብ ይበል፡፡ ይህን ስልም የወያኔ ሞት ይቀራል ማለት እንዳልሆነ ላሰምርበት እፈልጋለሁ፡፡ የወያኔ ሞት ወያኔ ስለጠላው ወይም እኛ ስለወደድነው የሚቀር ወይም የሚመጣ አይደለም፤ ታሪካዊ ሞት ስለሆነ ማንም ሊያግደው የሚችለው አይደለም፡፡ የወያኔ ሞት በተቃዋሚዎች መጠንከር ወይም መልፈስፈስ የሚወሰን አይደለም፤ ሁሉም የራሱ ጊዜ አለውና ወያኔ ከየትም አቅጣጫ በሚነሣ ወጀብና ሕዝባዊ ዐውሎ ንፋስ ይገረሰሳል፡፡ ዕዙ ከፈጣሪ በመሆኑ፣ መነሻው የሕዝብ ዕንባና ደም በመሆኑ የወያኔ ኅልፈት በማንም ምድራዊ ኃይል አይስተጓጎልም፡፡ ማዘግየትና ማፋጠን ግን ይቻል ይሆናል፡፡ ስለሆነም የትግል ሥልትን አዋጭ በሆነ መንገድ መቀየሱ ጉዳዩ ይበልጥ ከሚመለከታቸውና የእምዬ ኢትዮጵያን ነፃነት ለማዋለድ ታሪክ ከመረጣቸው ዜጎች ብዙ ይጠበቃል፡፡ እርግጥ ነው – የኢትዮጵያን ነፃነት እውን ለማድረግ በትንሹ ኢትዮጵያዊነት እንጂ የድርጅት አባልነት የግድ እንዳልሆነም መገንዘብ ተገቢ ነው፡፡ ሀገር የጋራ ናት፤ ፓርቲና ቡድን ግን የግል ናቸው – ሃይማኖትም፡፡ በመሆኑም ሁሉም የቻለውን ያድርግ፡፡ (የጠምባሮ ብሄረሰብ ብሂል ናት – አንድ ሰው የሞላ ወንዝ ዳር ቆሞ ወንዙ እስኪጎድልለት ድረስ ይጠብቃል – ሊሻገር፡፡ በዚህ መሀል ግንዱንና ደንጋዩን እያንከባለለ ከሚወርደው ጎርፍ ላይ ያ ሰውዬ ጠላቱን ያያል፡፡ በደስታ በመሞላትም አክ ይልና ምራቁን አጠረቃቅሞ እጎርፉ ላይ እንትፍ ይላል፡፡ የርሱ ምራቅ በጎርፉ ላይ ተጨምሮ ጠላቱን “ጠራርጎ” እስከመጨረሻው የወንዙ መዳረሻ እንዲወስድለት መሆኑ ነው፡፡ ልክ ነው! እኛም የዚህን ሰው አርአያ መከተል ይኖርብናል፡፡ የዋህነታችንና ፍርሀታችን በቃል ለማይገለጽ ውርደት ዳርጎናልና፡፡)

በዚህን ወቅት የሥልጣን ሱስ ሰለባውን፣ የፍቅረ ንዋይ ምርኮኛውን፣ ሰው መሣይ ድንጋይ ራሱን፣ አደናጋሪውን፣ አዘጥዛጩን፣ አሽቃባጩን፣ አስመሳዩን፣ አድር ባዩን፣ ከርሳሙን፣ ቂጥኛሙን፣ ውርዴውን፣ ነቀርሣውን፣ … መጠንቀቅ ይገባል፡፡ በዚህ በተዘበራረቀ ማኅበረሰብ ውስጥ ማንን ከማን ለይቶ ማመንና አለማመን ስለሚከብድ ብዙ ጥንቃቄ ያስፈልጋል፡፡ በተረፈ የወያኔ ሞት ከላይ እንጂ ከታች ብቻ ስላልሆነ እውን መሆኑ የግድ ነው፡፡ በሥነ ቃሉም “እንዲህ ጨሶ ጨሶ የነደደ እንደሆን፤ ያመዱ ማፍሰሻ ሥርፋው ወዴት ይሆን፡፡” መባሉ ለዜህ ነው፡፡

ማን ያውቃል፡፡ የአንዳርጋቸው በዚህ ባልተጠበቀ ሁኔታ ውስጥ መገኘት ለበጎ ቢሆንስ? የርሱን መሰዋት ግዴላችሁም ብዙም አንጥላው፡፡ ስንዴ ካልሞተች ለሌሎች ስንዴዎች ትንሣኤ መነሾ አትሆንምና – ድል ያለ መስዋዕት እንደማይጣፍጥም ይነገራልና የአንዳርጋቸው በወያኔ ወጥመድ ውስጥ መግባት ፈጣሪ ወዶና ፈቅዶ ያደረገው ይመስለኛል፡፡ እርግጥ ነው “አታሞ በሰው እጅ ታምር ሲይዟት ታደናግር” እንዲሉ ነውና ይህ ክስተት በኔና ባንተ ቢሆን ሊከብደን ይችላል፡፡ ይሁንና አንዳርጋቸው በነዚህ ጭራቆች እጅ መግባቱ ለበጎ ነው የምልባቸው ብዙ ምክንያቶች አሉ፡፡ ይሄውና ለዓመታት ሲጎሻመጡና ዐይንህ ላፈር ሲባባሉ የነበሩ አንዳንድ ተቃዋሚዎች – በቡድንና በድርጅትም በግለሰብም ደረጃ – የአንድነት መንፈስ ያሳዩት በዚህ ሰሞን ነው፡፡ ወያኔዎች ለአገዛዝ እንዲያመቻቸው ባዘጋጁት የክፍፍል አባዜ ሳይዘናጋ ወይም በቋሚነትም ይሁን በጊዜያዊነት ወደጎን በመተውና ግንቦትና ሚያዚያ ሳይባባል ምድረ አበሻ ከጫፍ እስከ ጫፍ የተነቃነቀው በዚህ ሰሞን ነው – የሚያስቀና ነውና ያዝልቅልን፡፡ “የትም ብኖር ለካንስ ወያኔ ከፈለገ አንገቴን ጨምድዶ እንደፈለገው ሊያደርገኝ ይችላል” ከሚል ስሜት በመነሳት ይመስላል አበሻ ሁላ መከፋፈሏን እየናቀች ወደጋራ መድረክ የመጣችው በዚሁ ሰሞን ነው – እንዳንዳንዶቻችን ግምት ለጊዜያዊ የፕሮፓጋንዳ ፍጆታ ሊሆን ይችላል ብለን ብንጠራጠርም፡፡ ሌላም ሌላም፡፡ እንደዚህ ሰሞኑ ትብብርና መተሳሰብ ቢሆን ኖሮ ወያኔዎች ወደደደቢታቸው ከተመለሱና ከናካቴውም ከከሰሙ በትንሹ 30 ዓመታትን ባስቆጠሩ ነበር – ግና የኛ ኃጢኣትስ በምን ሥርየትን ያግኝ? እንዴትስ ይከፈል? ሁሉም ነገር ለበጎ ነው፡፡ ከዚህ አንጻር ታዲያን የአንዳርጋቸው ጭዳነት ለመልካም ፍጻሜ ቢሆንስ? ፈጣሪ ሌላ መንገድ ከመፈለግ ይልቅ ይህኛውን የወዲያው መንስኤ (immediate cause) ፈቅዶትስ ቢሆን? አላውቅም፤ ግን እንዲህ ያለ ነገር ይሰማኛል – ስሜት የድርጊትን ያህል ከባድ ባይሆንም፡፡ በታሪክ ትምህርት ለአንድ ኹነት መነሾ ሁለት መሠረታዊ ምክንያቶች እንዳሉ ይነገራል – fundamental and immediate causes ይሏቸዋል – መሠረታዊና የወዲያው መንስኤዎች ልበላቸው፡፡ የአንደኛውን ይሁን የሁለተኛውን የዓለም ጦርነት ያስነሳችው በሰው ማሣ የገባች አንዲት ቀበጥ ዓሣማ እንደሆነች ሲነገር ሰምቻለሁ፡፡ ለአንድ የቦካ ቂም እውናዊ ትንሣኤ አንዲት ቀጭን ሰበብ ታስፈልጋለች ማለት ነው፤ የአንዳርጋቸው ግን ከቀጭንም በላይ እርፍ እሚያህል ነውና በቃላት ብቻ የሚያልፍ እርግማንና ቁጣ ሰቆቃን ከማባባስ ውጪ የሚፈይደው ነገር እንደሌለ መረዳት ይኖርብናል፡፡

አንዳርጋቸው በአረመኔዎቹ እጅ ከገባ በኋላ በደከመ አንደበት “blessing in disguise” ሲል ሰምቻለሁ፡፡ በወያኔዎቹ ትርጓሜ እንዲህ ማለቱ “መያዜ ዕረፍት ሰጥቶኛልና ከእንግዲህ እኔ እንዳረፍኩና ሰላም እንዳገኘሁ እናንተም አርፋችሁ በመቀመጥ ሰላማችሁን አረጋግጡ” ለማለት እንደፈለገ እንዲገባን የፈለጉ ይመስለኛል፡፡ እውነተኛውን ትርጓሜ ጊዜ ይነግረናል፡፡ አንዳርጋቸው ግን የቆርጦ ቀጥሎቹን ወያኔዎች ምኞት የሚያስተናግድ ንግግር እንደማያደርግ ከግምት የሚልቅ እምነት አለኝ፡፡ ለነገሩ እንደዚያም ቢሆን አይገርመኝም፡፡ ወያኔዎችን ለሚረዳ ሰው፣ አንድን ሰብኣዊ ፍጡር ከሰይጣንም በላይ ሰይጣን በመሆን እንዴት እንደሚያሰቃዩና በዘመናዊ መንገድ ሂፕኖታይዝ በማድረግም ጭምር ከአንድ አእምሮ ምን ዓይነት ግብኣት ጨምረው ምን ዓይነት መረጃ ሊያወጡ እንደሚችሉ እረዳለሁ፡፡ ዘመኑ በስይጣኔ (በስልጣኔ አላልኩም) እጅግ የተራቀቀ ነው፡፡ በአርትዖት (ኤዲቲንግ) መቁረጥ መቀጠሉ እንዳለ ሆኖ እንደፈረንጆቹ ከሆነ በአእምሮን መቆጣጠሪያ ዘዴ (ማይንድ ኮንትሮል ሲስተም) የአንድን ሰው አእምሮ ሙሉ በሙሉ በመቆጣጠር የፈለጉትን መረጃ ከትተው ሲያበቁ ሰውዬው ያንኑ እንዲናገር የማድረግ ሰይጣናዊ ችሎታ አላቸው፡፡ ደርግም በጊዜውና ቤት ባፈራለት የማሰቃያ መንገዶች  “አልጋችን ሥር ታንክ ደብቀናል” የሚያስብል ወፌላላና የዘይት ጥብሳት እንደነበረው እናስታውሳለን – አለመታደላችን ግን ምን ያህል የበረታ ነው! ወያኔማ ከዚያ የሚብስ እንዴት አይኖረው! ለማንኛውም በበኩሌ የአንዳርጋቸውን ፈረንጃዊ ፈሊጥ ለኔ በሚስማማኝ መልኩ በመጋራት ይህ ሁኔታ ለኢትዮጵያ “mixed blessing” ነው እላለሁ፡፡ ከእንግዲህ መጨነቅ ለኛው ነው፡፡ አንዳርጌ ግዳጁን ተወጥቷል፡፡ ስለሱ ማላዘንም ይብቃ፡፡ በአንዳርጋቸው እጅ መዛል ምክንያት ከእጁ ያመለጠችዋን ባንዲራ ተረክቦ መታገል ይገባናል፡፡ ልቅሶና ዋይታ ሆድ ከማስባስና ወደኋላ ከመጎተት በስተቀር ማንንም አይጠቅምም፡፡ ሀበሻነትን ለጊዜው ገታ አድርገን ፈረንጅ እንሁንና ጥርሳችንን ነክሰን አቀበቱን እጅ ለእጅ ተያይዘን በኅብረት እንውጣ፡፡ ባይሆን ሁሉም የዚህ ቲያትር ተካፋይ የየራሱን ሒሳብ የሚያወራርድበትን ቀመር አዘጋጅቶ ማስቀመጥ ነው፡፡ የመንም፣ ወያኔም፣ … በዚህ ቆሻሻ ተግባር የተሳተፈ ሁሉም ፍጡር ዋጋውን እንደሚያገኝ በበኩሌ ጥርጥር የለኝም፡፡ የኢትዮጵያውያን ጊዜ ሲመጣ የ”ለለአሃዱ በበምግባሩ” ፍትህ ይበየናል፡፡

ወያኔዎች ጨካኞች መሆናቸውን እናውቃለን፡፡ በአንዳርጋቸው ላይ ምን ሊያደርጉ እንደሚችሉም በጣም ግልጽ ነው፡፡ ነገር ግን ማስታወስ የሚገባን ነገሮች አሉ፡፡ የትግራይ ወንበዴዎች ትግሉን ለተወሰነ ጊዜም ቢሆን ያኮላሹ መስሏቸው አንዳርጋቸውን ሊገድሉት ይችላሉ – ምድር ላይ ገና ባልተሞከሩ የማሰቃያ ሥልቶች ማሰቃየታቸው እንደተጠበቀ ሆኖ፡፡ አሰቃዩትም ገደሉትም ከእንግዲህ ዕዳው የነሱና የኛ እንጂ የአንዳርጋቸው አይደለም፡፡ አንዳርጋቸው ከዕዳው ነፃ ነው የምለው ሥራውን ጨርሷል በመባሉ አይደለም፡፡ በእጅህ የገባን ብርጭቆ ስትፈልግ መስበር፣ ሳትፈልግ ማስቀመጥ ያለብህ አንተ ስለሆንክ አንዳርጋቸውን እንደፈለጉ የማድረግ ዲያብሎሳዊ መብትና ሥልጣን ያላቸው ወያኔዎች ብቻ ናቸው፡፡ ለምን አስያዙት ብሎ መቆጣትም ሞኝነት ነው፡፡ እንዲያውም ቂልነት፡፡ አንዳርጋቸው ዓለምን የሚዞረው ለወያኔዎች ዕቅፍ አበባ ለማበርከት አለመሆኑ መታወቅ አለበት፡፡ ከዚህ አኳያ ለምን ያዙት ብሎ መናደድ ጉንጭ አልፋና ለትዝብትም የሚዳርግ ነው፡፡ የሚያናድደው የተያዘበት አኳኋን ነው፡፡ ያመኑት ፈረስ በደንደስ መጣሉ ነው እጅግ የሚያበግነው፤ ዓለም አቀፍ ህግ መጣሱ ነው የሚያንጨረጭረው፤ ሊያስቀሩት ይቻል በነበረ የአደጋ ሥጋት አጉል መስዋዕትነት መክፈሉ ነው የእግር እሳት፡፡ በጦርነት ቢሆን እሰዬው ነው – የአሁኑን ያህል ቁጭትና ንዴት የለበትም፡፡ ለዚያ ሰሞኑን ለደረሰው ጥፋት ደግሞ የአንድ ወገን ብቻ ሣይሆን የብዙ ወገኖች ጥፋት ይመስለኛል – ትምህርቱ ቆንጣጭና አስቆጪ መሆኑ ከፋ እንጂ ይህ ክስተት መማሪያ ነው፡፡ ደግሞም ከፍ ሲል ለመጠቆም እንደሞከርኩት የፈሰሰ አይታፈስምና ስህተትን በመከፋፈልና በመጸጸት ጊዜን ማባከን ተገቢ አይደለም፡፡ የሆነው ሆኖኣል – የሆነውም ሊሆን ግድ ስለሆነ መሆኑን ማመን ይገባል፡፡ የማይሆን ቢሆን ኖሮ ቀድሞውንም አይሆንም ነበርና፡፡ እናም ጉዞ ወደፊት እንጂ ወደኋላ የለምና ይልቁንስ የተሰዋው ወንድማችን አስተዋፅዖ ከግቡ እንዲደርስ እንጣር፡፡ ተሰዋ ስልም በርግጥም እስካሁኒቷ ሰዓት ተሰውቷል ለማለት ሳይሆን የወያኔ እጅ የገባ ሰው የድመት ምርኮኛ የሆነ ያህል ስለሚሰማኝ ነው፤ እንጂ ከንፍሮ ጥሬ ይወጣልና እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ አንዳርጋቸውም የነገን ጣይ ሊያይ የሚችልበት ጠባብ ዕድል ሊኖር ይችል ይሆናል – ወያኔዎች ማሰብ ከጀመሩ፣ አሁን ዘግይተውም ቢሆን በመጨረሻ ሰዓታቸው ወያኔዎች ሰው መሆን ከጀመሩ ይህም ቀላል ነው፡፡ ተያይዞ ከመጥፋት ቢያንስ ለትውልዳቸው ሊያስቡ ከፈለጉ እያንዣበበ የሚገኘውን የጥፋት ደመና ከወዲሁ ሊያስቀሩት ይችላሉ፡፡ እኔ ግን አይመስለኝም፡፡

ወያኔዎች ወደፊትን መመልከት የማይችሉ ደናቁርት መሆናቸው ከአንዳርጋቸው ሕይወት አንጻር ያሳዝነኛል፡፡ የሚያሳዝነኝ አንዳርጋቸው ሳይሆን የወያኔዎች ድንቁርና ነው፡፡ የሁልጊዜ ትምክህታዊ መርሆኣቸው “ማን ምን ያደርገናል? ተልባ ቢንጫጫ በአንድ ሙቀጫ…” የሚለው አፄያዊና ደርጋዊ ትዕቢታቸው ነው፡፡ አሁንና ከአሁን በኋላ ግን ይህ ትምክህት አይሠራም፡፡ ለሁሉም ጊዜ አለው፡፡ ለመፍራት ጊዜ አለው – ለመጀገን ጊዜ አለው፤ ተስፋ ለመሰነቅ ጊዜ አለው – ተስፋ ለመቁረጥ ጊዜ አለው፤ ለመለያየት ጊዜ አለው – ለመተባበር ጊዜ አለው፤ ለመጣላት ጊዜ አለው – ለመታረቅ ጊዜ አለው፡፡ ይህን ነባራዊ ዘመን የማይሽረው እውነት ቅዱሳት መጻሕፍትም ቀድመው አስቀምጠውታል፡፡ በአሁኑ ወቅት ለወትሮው በፈሪነትና በልዩነቶች ተከፋፍሎ በመራኮት ዘመን አመጣሽ ወያኔ ወለድ ጠባዩ ወያኔዎች ይፈርጁት የነበረው የኢትዮጵያ ሕዝብ ወደ ቀደመው አንድነቱ እየመጣና ቁጭቱን ለመወጣት መንገድ አመላካች ሙሤ እየፈለገ ነው፡፡ ስለዚህ አንዳርጋቸውን መግደል ከጥቅሙ ይልቅ ጉዳቱ እንደሚያመዝን እነሱ ባይገባቸው የምናውቅ ወገኖች ጠንቅቀን እናውቃለን – ይህን ስል እንዳይገድሉት በውስጠ ወይራ ለመለማመጥ አይደለም – ወያኔዎች ልምምጥና ልመና እንደማይገባቸው አውቃለሁ፤ ወያኔዎች ያሸነፉትን በመግደል የሚረኩ ጅሎች እንጂ አንድም የጀግንነትና የመሐሪነት መንፈስ እንደሌላቸውም አውቃለሁ፡፡ ጅብ ለማንም እንደማይራራ ወያኔም ከጅብ በበለጠ የራሱን ተጋዳዮች ሳይቀር እየቀረጠፈ ነው እዚህ የደረሰው፡፡ ጅብ እንኳን ጓደኞቹ ሲቆስሉና ሲሞቱ ነው አሉ እሚበላቸው፡፡ ወያሜዎች ግን አንድን ሰው ለመብላት በተቃዋሚነት መጠርጠርና በጠላትነት መፈረጅ ብቻ በቂያቸው ነው፡፡

ሴትዮዋ “መንግጌ አባስኩሽ” እንዳለችው ነው፡፡ የወያኔዎች የኅልውና ማስጠበቂያ ሥልቶች በሙሉ ታኝከው አልቀዋል – ባለፉት ሠላሳ ምናምን ዓመታት ዕድሜያቸው የመግዥያ ሥልቶቻቸውን አንድ በአንድ አኝከው በልተው ጨርሰዋቸዋል፡፡ መግደልም፣ ማሰርም፣ ማሰቃየትም፣… ሁሉም ፋሽኑ አለቀ፡፡ የሞተን ሰው የማትገድልበት፣ የሞተን ሰው የማታስርበት፣ የሞተን ሰው የማታሰቃይበት ጊዜ ሊመጣ እንደሚችል ማወቅ ይኖርብሃል – እንደዚያ ያለ ሰው ከሆንክ፡፡ እርግጥ ነው – ወያኔዎች የሚያሰማሯቸው የሕወሓት ወጠምሻ ድንጋይ ራሶች ሆዳቸው እስከሞላ ድረስ አንጎል የሚባል ነገር ስለሌላቸው ከመግደልና ከማሰቃየት ወደኋላ አይሉም – በዚያ ላይ እንዲያደፋፍሯቸው የሚጠቀሙባቸው አንዳንድ ንጥረ ነገሮች ሳይኖሩ እንደማይቀሩ እገምታለሁ – ለምሳሌ ሀሺሺንና ጫትን መጠጥንም የመሳሰሉ፡፡ ደግሞም ብዙ ትግሬ ካድሬዎች – ስታዘባቸው – ቂላቂል ናቸው፡፡ ለድርጅታቸው ያላቸው ታማኝነት የማምለክ ያህል ነው – ከዚያም በላይ፡፡ በየመጠጥ ቤቱ በጣራ መለስ ጩኸት ሲያውካኩ ስትሰማ – በዚያም ጩኸት ኢትዮጵያዊነትን የሚያራምዱ ወገኖችን እንዴት ሲሳደቡና ሲወርፉ ስታዳምጥ በርግጥም እነዚህ ሰዎች ወያኔ እስከወዲያኛው በሥልጣን ፀንቶ እንደሚኖር የሚያምኑና አድርጉ የተባሉትን ሁሉ ያለማቅማማት እንደሚያደርጉ ትገነዘባለህ – ተገንዝበህ ብቻ አታበቃም – ካዘንክባቸው በኋላ ታዝንላቸዋለህም፡፡ “አንድ ሰው ምን ያህል አእምሮው ከሥራ ውጪ ቢሆን ነው በሰው ስቃይ የሚደሰተው?” ብለህ ራስህን ስትጠይቅ የዓለም ወቅታዊ ቅርጽ ከሦርያ እስከ ሶማሊያ ፊትህ ላይ ድቅን ሊልብህ ይችላል – ሊያውም ለዘመናት አብሮ በኖረው ወገኑ ላይ፡፡ ችግሩ የሚከፋውና ተስፋህን የሚያሟጥጥብህ ደግሞ ድርጅታቸውን በጭፍን ስለሚወዱና – ይህም ለሆድና ለዘውጋዊ የዓላማ ጽናት ሲሉ ነው – ኢትዮጵያዊነትን ፈጽመው እንዲጠሉ ስለተደረጉ ከነዚህ ሰዎች ጋር መነጋገርም ሆነ መደራደር የማይቻል የማይሞከርም የመሆኑ መጥፎ አጋጣሚ ነው፡፡ ሰው ግን በስንት ይበደላል!

አንዳርጋቸው ቢገደል አፈር አያሟሽም፡፡ አንዳርጋቸውን ቢገድሉት አንድ ነገር ይቀርበታል፡፡ ያም በጉጉት ይጠብቃት የነበረችዋን የኢትዮጵያን ነፃነት ሊያይ አለመቻሉ ብቻ ነው፡፡ ወያኔዎች ቢገድሉት ይህን የአንዳርጋቸውን ጉጉት ባጭር ለማስቀረት ካላቸው ፍላጎት እንጂ ዕድሜያቸውን ለማርዘም የርሱ ሞት ጠቃሚ ሆኖ እንዳልሆነ እስካሁን ካላወቁት አሁኑኑ ሊያውቁት ይገባል- በቃ፤ እውነቱ ይህ ነው፡፡ እንጂ አንዳርጋቸውን በመግደል የኢትዮጵያን ነፃነት እናስቀራለን የሚል አስተሳሰብ አሁንም ካላቸው በርግጥም በዱሮው ጅልነታቸው እንደታሰሩ ናቸው ማለት ነው፡፡ የተቆረጠን ቀን የአንድ ሰው መሞት አለመሞት አይመልሰውም፡፡ አያድርግበትና ቢገድሉት እንዲያውም ኢትዮጵያ ትጠቀማለች፤ ወያኔ ግን ክፉኛ ይጎዳል፡፡ አንዳርጋቸው በአንዳርጋቸውነቱ ቢሞት ባይሞት ምንም ማለት እንዳልሆነ ግልጽ ነው – ወንድ ሲናገር ዛሬ ጧት ከኢሳት እንደሰማሁት አንዳርጋቸው በሕይወቱ የደላው ሰው አልነበረም – በሀገሩ ፖለቲካዊ ቀውስ ሳቢያ ከገሞራው ኃይሉ(ኃይሉ ገሞራው?) ብዙም ያልተሻለ ሕይወት ይመራ እንደነበር ተገንዝቤያለሁ፤ ኢትዮጵያን ያለ – ስለኢትዮጵያ አብዝቶ የተጨነቀ ተጠቅሞ አያውቅም – ምን ሩቅ አስኬደኝ … ነገን በተስፋ ሲጠብቁ ይህች ቅጽበታዊ ምድራዊ ዕድሜያቸው እየከዳቻቸው ያሉ በየሽርንቁላው ተወትፈው ቅዳሜን እሁድ ለማድረግ የሚታትሩ በርካታ ልጆች አሏት – ኢትዮጵያ፡፡ አንዳርጋቸው የሚለየው ጥሪውን ተቀብሎ የድርሻውን አበርክቷል – እናም አይቆጨውም፡፡

የርሱ ነገር መንጠልጠያው በትንሹ የሰባና የሰማንያ ሚሊዮን የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው፡፡ አንዳርጋቸውን ሲገርፉ ኢትዮጵያን እየገረፉ ነው፡፡ አንዳርጋቸውን ሲያሰቃዩ ኢትዮጵያንና ኢትዮጵያውያንን እያሰቃዩ ነው፡፡ የአንዳርጋቸውን ጥፍር ሲነቅሉ የኔንም ጥፍር እያወለቁ ነው – ልዩነቱ የኔ በስሜት ነው – የርሱ ግን በውነት ነው፡፡ ይህ ደግሞ የዞረ ድምር አለው፡፡ ዛሬ አንዳርጋቸውን የሚያሰቃዩ ሰዎች ደናቁርት ይሁኑ እንጂ እነሱም የሚሰቃይና የሚሞት ሰብኣዊ አካል ወይም ሰውነት አላቸው፤ ቤተሰብ አላቸው፤ ቀጣይ ትውልድ አላቸው፤ ሀብት ንብረት አላቸው፤ ባያምኑበትም ኢትዮጵያዊ ማንነትና ሥረ መሠረት አላቸው፡፡ ስለሆነም በነገይቷ ኢትዮጵያ በነሱና የነሱ በሆነ ነገር ላይ ሁሉ ምን ሊደርስ እንደሚችል ከአሁኑ ሊገምቱ ካልቻሉ በርግጥም ኅሊናቸው ታውሯል፤ አንጎላቸውም ተሰውሯል ማለት ነው፡፡ ዘመድ የሚያስፈልገው ይሄኔ ነው፡፡ መካሪ ያስፈልጋል፡፡ አንዳርጋቸውን መግደል ያዋጣ የነበረው ዛሬ አይደለም – ቀደም ሲል ቀረ፡፡ እርሱን ከመግደልም ይልቅ የዐዋቂዎችን ምክር ሳይንቁ ቢሰሙና ሥልጣን ከያዙ ጀምሮ እያደረጉ የመጡትን ዘግናኝ አፍራሽ ነገሮችን ባያደርጉ፣ ለሕዝብ ስሜት ቢገዙ፣ የሕዝብን ፍላጎት ቢያከብሩ አንድ አንዳርጋቸውንና ከርሱም በፊት ያረዷቸውን ሚሊዮን ኢትዮጵያውያንን ሳይረፈርፉ ከኢትዮጵያውያንና ከከራማዋ ጋር ታርቀው በቀላሉ በሰላም መኖር በቻሉ ነበር፡፡ አሁን ግን በጣም መሽቷል፤ ድንግዝግዝ ብሎባቸዋል – ከፈጣሪና ንጹሓን ፍጡሮቹ ጋር ደም ተቃብተው ከሰማዩም ከምድሩም ጋር ክፉኛ ተቀያይመዋል፡፡ አንዳርጋቸው ሌላ ኃጢኣትና ወንጀል ኖሮበት ሳይሆን በትንሹ የሚከተሉት ነገሮች እንዲወገዱ ነው የታገለው፡፡ እንደማሣረጊያ ከመቶ የትግሬ ወያኔ ጥፋቶች ዜሮ ነጥብ ዜሮ ዜሮ አንዱን ብቻ እዚህ ላይ ማስታወስ ፈለግሁ፡፡ ቀናና የመልካም ሥነ ምግባር ባለቤት የሆን ትግሬዎች በዚህ የወያኔዎች ዕኩይ ድርጊት ልናዝን እንጂ ባላደረግነው ነገር የቀያችን ልጆች ስላደረጉት ብቻ ልናፍር አይገባም፡፡ ክፉ ሥራና ኃጢኣት በዘርና በጎሣ አይተላለፍም፡፡ ሁሉም እንደሥራው እንጂ በጎጣዊ ማንነቱ ፍርድን አይቀበልም፡፡ እነዚህ ኢትዮጵያን ከእግር እስከራስዋ ወርረው እስከመቅኒዋ ድረስ እየመጠመጡ የሚገኙ ሰዎች ኅሊና ብሎ ነገር፣ ሀፍረት ብሎ ነገር፣ ይሉኝታ ብሎ ነገር አልፈጠረባቸውምና አንዳርጋቸውን ቆራርጠው ቢበሉት ለጊዜውና አሁን የአማርኛውን ጉድ “ጉድ!” ከማለት ውጪ ሌላ ቃል የለንም፡፡ የነገውን ግን አንድዬ ነው የሚያውቅላቸው፡፡

አዲስ አበባ ውስጥ የአንድ ቀበሌ ሥራ አስፈጻሚ ያደረገው ተዓምር ይህ ነው፡፡ ከበላዮቹ  ለአንድ ሹመት አንድ ባለዲግሪ መርጠህ ላክ ይባላል፡፡  ይህ ሰው ባለዲግሪ ትግሬ ቢያፈላልግ ያጣል፡፡ ምሥጢሩን የተረዳ አንድ ከርታታ አማራ “እኔ የሚፈለገው ዲግሪ አለኝ አይደለም እንዴ ለምን አትልከኝም?” ብሎ ይጠይቀዋል፡፡ ምን መለሰለት መሰላችሁ – “ያንተን ዲግሪ ለሽንት ቤት ተጠቀምበት!”፡፡ ያ ቆፍጣና ካድሬ አንዷን ባለዲፕሎማ ትግሬ ላከና ዐረፈው፡፡ ትግሬ ሁን እንጂ፣ በዚያም ላይ ታማኝነትን ደርብበት እንጂ መማር አለመማርህ ዋጋ የለውምና ሥራ ለመያዝ በባለዲግሪዎች የሌሎች ዘውጎች ተቀጣሪ አሽከሮችህ ላይም ለመዘባነን የሚያሳስብህ ነገር የለም – ተዓምር ነው፤ ከተዓምርም በላይ፡፡ የዚህ ሁሉ ጎጠኝነት መንስኤ ሥራ በትክክል ተሠራ አልተሠራ ወያኔን የማያስጨንቀው መሆኑ ነው – የሚያስጨንቀው ፖለቲካውንና ጥቅሙን ከወያኔ ትግሬ ውጪ ሌላ ኢትዮጵያዊ መያዙ ነው፡፡ ያ ያንገበግበዋል፡፡ ኢትዮጵያ ማለት ትግሬ፣ ትግሬ ማለት ኢትዮጵያ ሆናልሃለች፡፡ በሁሉም የመንግሥት መ/ቤቶች በአዛዥ ናዛዥነት እንደልቡ የሚፈነጥዘው ትግሬ ወያኔ ነው፡፡ ሌላው ባይተዋር ነው – ጨዋ ኢትዮጵያዊ ትግሬም ጭምር፡፡ በተለይ አማራ ለዘበኝነትም የማይታመን ሆኖልሃል ወዳጄ! አማራ “የሥራውን ነው ያገኘው፤ እሰይ! እንኳን!” እንዳልል ይህ ዘውግ በዚህን (ወያኔዎች በሚያሳዩት ደረጃ) ያህል ድፍረትና በዚህን ያህል ክትሩን የለቀቀ ጀብድ ኢትዮጵያን በግሉ ተቆጣጥሮ የጋጠበት፣ ሌሎችን በዚህን ያህል ደረጃ ያዋረደበት አንድም የግል ተሞክሮም ይሁን ታሪካዊ የጽሑፍ ማስረጃ ላገኝ አልቻልኩም፤ እናም ለመፍረድ ተቸገርኩ፡፡ እዚያው አጠገባቸው ስለምኖር ይህን አውቃለሁ፡፡ ፍርድ ለራስም ነውና በምለው ነገር እርገጠኛነቴን አትጠራጠር፡፡ እንዲህ የምለው ለዲያስጶራው እንጂ የዚሁማ የዚሁ ነው፡፡ እዚህ ያለውማ ነጋ ጠባ የተለማመደውን መራር እውነት እኔ ላረዳው ይቻለኛልን?

አንድ የኢሕአዴግ አባል የሆነ አማራ ያደረገው ተዓምር ይህ ነው፡፡ ይህ ሰው እንዲህ የሚል የቅጥር መመሪያ በውስጥ ማስታወሻ ይደርሰዋል፡- “ ስትቀጥር 50 በመቶ ትግሬ፣ 25 በመቶ ደቡብ፣ … 1 በመቶ አማራ …” ይህ አባል ትግሬ መስሏቸው ሊሆን እንደሚችል መገመት ይቻላል – ብዙዎቹ ትግሬ ካድሬዎች ይሉኝታ ስለሌላቸው ጅሎች መሆናቸውን ልብ ይሏል፡፡ ያ የኢሕአዴግ አማራ ካድሬ ብልጥ ነበርና አመልካቾች ሲመዘገቡ አማራ ነን የሚሉትን በጆሯቸው ጠጋ እያለ “ሃድያ ነኝ ብለህ ተመዝገብ”፣ “ጠምባሮ ነኝ በል”፣ “ኮንሶ ብለህ ተመዝገብ” … በማለት ምድረ አማራን በደቡብ ስም ከደቡቦቹ ጋር እያዛነቀ ቀጠረ አሉ፡፡ ምን ያድርግ፤ ጅብ ከሚበላህ በልተኸው ተቀደስ ይባል የለም? በዚህ መልክ ብቀጥል አውሎ ያሳድረናል፡፡ ይህንን ዐይን አውጣ የወያኔ ዕኩይ ተግባር ለማስተካከል መሞከር ሽብርተኛ ካሰኘ የነሱ ምን ሊባል እንደሚችል ራሳችሁ ገምቱ፡፡ ጎበዝ፣ ኢትዮጵያዊነት እንዲህ እንደወያኔ ከሆነ ባፍንጫየ ይውጣ፡፡ ከእንስሳትም ወረዱብኝ፡፡ …

ተዓምረ ወያኔ ከዚህም ከዚያም

  • ኃ/ማርያም ደሳለኝ የትሮይ ፈረስ ሆኖ በውስጡ ያሉት እነሐጎስና እነግደይ ናቸው፡፡ ኃ/ማርያም ከሁለቱ የኢትዮጵያ መንግሥታት የአንደኛው አሻንጉሊት ነው – ኢትዮጵያ የኅቡዕና የግልጽ ሁለት መንግሥታት እንዳላት የማያውቅ መቼም የለም – የነጎይቶምና የነአብረኸት የመጋረጃው በስተጀርባ መንግሥትና የነደቻሳና የነስንሻው የምስለኔና እንደራሴ የውክልና መንግሥት፡፡ የኃ/ማርያም አሻንጉሊትነት “ኢትዮጵያ ከደቡብ ሕዝቦች የመጣ ጠ/ሚኒስትር አላት” የሚል ቅባት በተለይ ለደቡቡ ሕዝብና ለውጪው ዓለም ማደናገሪያነት መቀመጡ ነው፡፡ እንጂ ስለኢትዮጵያ የወቅቱ አስተዳደር ቅንጣት አያውቅም – እንዲያውቅም አይደረግም፤ ለታይታ ካገለገለ እርሱ ምን ቤት ሆነና! ግን ወግ አይቀርምና በሚዲያቸው “ጠ/ሚኒስትር ኃ/ማርያም ከቻይናው አቻቸው ከቺንግቹዋ ቹንግ ጋር ተወያየ፡፡ ጠ/ሚኒስትር ኃ/ማርያም ስለታላቁ የህዳሴ ግድብ ከግብጹ አቻቸው ከፕሬዚደንት አልጉልቤ ሲሲ ጋር ተነጋገሩ …” ይባልልኛል፡፡ ቂቂቂቂቂ ….. አለች ያቺ ጋዜጣ ጽሑፋዊ ሳቋ አምልጧት፡፡ የቃሉ አጠራር በጠያፍነቱ ምክንያት ባያስነውረኝ ኖሮ ኃ/ማርያምን “ኮንዶም ነው” ባልኩና ደስ ባለኝ፡፡
  • የአደባባይ ምሥጢር፡፡ መከላከያ፣ ውጭ ጉዳይ፣ ፖሊስ፣ ደኅንነት፣ ጉምሩክ፣ የመንግሥት ባንኮችና ኢንሹራንሶች፣ መብራት ኃይል፣ ቴሌ፣ የትምህርት ተቋማት፤ ገቢና ወጪ ንግዶች፣ የግንባታና የልማት ድርጅቶች፣ ፋብሪካዎች፣ ሆስፒታሎች፣ ክፍለ ከተማዎች፣ ወረዳዎች፣ አነስተኛና ጥቃቅኖች፣ ሱቆች፣ መጋዘኖች፣ ማከፋፈያዎች፣ ፋብሪካዎች፣ ኢንዱስትሪዎች፣ ወዘተ. ሙሉ በሙሉ በትግሬ ወያኔዎች ቁጥጥር ናቸው – የሌሎች ዘውጎች አባላት በታዛዥነት መኖራቸው አያስገርምም – ከተላላኪነትና ከእንደራሴነት የዘለለ ሚና የላቸውም ግን፡፡ ኢትዮጵያ በትግሬ ወያኔዎች የወለድ አግድ ማነቆ ሼር ናት፡፡ ተናደድ፤ መናደድ ባንተ አልተጀመረም፡፡ ስትናደድ ወደ ለውጥ የሚያመራ መንፈስ ይመጣልሃል – ምናልባትም ጥሩ መንፈስ፡፡
  • በግል ትምህርት ቤቶች በውድ ዋጋ ከሚማሩ ተማሪዎች መካከል በግምት ከመቶ 95 የሚበልጡት ወላጆቻቸው ትግሬዎች ወይም ኢሕአዴግ ከሚባለው የወያኔ ዋሻ አንዳች ፍርፋሪና ዳረጎት የሚጣልላቸው ውዳቂ ዜጎች ናቸው፡፡ ደግሞም ለትምህርት ዋጋ የማይሠጡ ደናቁርት ናቸው፡፡ ልጆቻቸው ቢማሩ ባይማሩ ደንታቸው አይደለም፡፡
  • በየትም ሥፍራ በተለይም በአዲስ አበባ ከሚሠሩ ህንፃዎችና የልማት አውታሮች ውስጥ አሁንም በግምት ከ80 ከመቶው የሚበልጡት የትግሬዎች ናቸው፡፡
  • አዲስ አበባና መቀሌ ልዩነታቸው ፍጹም እስከሚጠፋ ድረስ ሁሉም የአዲስ አበባ ንግድ ቤቶች በትግሬ ወያኔዎች ቁጥጥር ሼር ሊገቡ የቀራቸው ጊዜ ግፋ ቢል ከአሁን በኋላ አሥር ዓመት ቢሆን ነው – እንዲያውም ከዚያም ያንሳል፡፡  የትም ሂዱ፣ የትም ግቡ ባለሱቁና ባለመኪናው ባለሀብቱና ባለቀብራራ ኑሮው ትግሬ ነው፤ ገንዘቡን የሚመነዝረው ትግሬው ነው፤ ለሚስቱ ብቻ ሳይሆን ለየውሽማውም ሳይቀር የሀገራችንን ሀብት መኪናና ቤት በመግዛት የትም የሚረጨው ትግሬው ነው፤ ሕዝብ ቆሼ ተራ ሀብታም በጣለው ፍርፋሪ ላይ ሲራኮትና ዜጋ በየመንገዱ ወድቆ በርሀብ አለንጋ ሲገረፍ ወያኔ ትግሬዎች በልጆቻቸው የልደት ቀን በሚሊዮን የሚገመት ገንዘብ ለድግስና ለስጦታ ያወጣሉ – ድንቁርና ከዚህ በላይ ካለ ንገሩኝ፡፡ ዜጎች በርሀብ እየወደቁ፣ ተማሪዎች በርሀብ ምክንያት መማር እያቃታቸው በምሣ ሰዓት በየትምህርት ቤቱ ኮሪደር እየተዘረሩ፣ የለማኙ ቁጥር ከመጽዋቹ ቁጥር በልጦ ኢትዮጵያ የቧጋቾች ሀገር ሆና ጥቂት ወያኔ ትግሬዎችና አንፋሽ አከንፋሾቻቸው ለራሳቸው እንደምትመጥን አድርገው በፈጠሯት አዲሲቷ የወያኔ ኢትዮጵያ ውስጥ ልዩ ምድረ ገነት ፈጥረዋል፡፡ የሌሎች ዘውጎችን ነጋዴዎች የቤት ኪራይ በመቆለልና ከአቅማቸው በላይ የሆነ ግብር በመጣል ከንግዳቸው አባርረው፣ መኖሪያ ቤታቸውንም እንዳመቺነቱ በዘረፋና ወይም በግዢ ነቅለውና ፈንቅለው የአሁኑ የአዲስ አበባ ጠረን ትግሬ ትግሬ የሚል ሆኗል፡፡ ቦሌም ግባ ጉለሌ “ጥሩ ጥሩ ለትግሬ” በሚል ሥውር ዐዋጅ ሌላው ከሥሩ ተፈንቅሎ ለስደትና ለማራሪነት ሲዳረግ ወያኔዎች ገብተው ይዝመነመኑበታል – ይህንን ሁሉ ግፍ የማይቆጥርና ዕዳን የማያስከፍል ፈጣሪ የለም የምትሉ ከሆነ እኔ የለሁበትም፡፡ የፍርድ ቀን ከመምጣቱ በፊት ወያኔ ትግሬዎች ሆይ አቅል ጀባ!
  • ምሥኪን ዜጎች ብሶታችንን እንዳንናገር እንኳ ንግግርን፣ አስተሳሰብንና ሃሳብ ማውጠንጠንን ራሱን በሽብርተኝነት የሚያሳስር ወንጀል እንደሆነ አስደርገው በወኪሎቻቸው የመንግሥት ወያኔ ትግሬዎች አማካይነት በሚያስወጧቸው የወሮበሎች ህግጋት በቁማችን መቀመቅ ሰደውናል፤ እንዳንታሰር እንፈራለን – ስለምንፈራም ፀጥ ረጭ እንላለን፤ ፀጥ ረጭ ስንልም ወደንና ፈቅደን የምንገዛላቸው ይመስላቸዋል፡፡ ገደብ የለቀቀውን “ትግስታችንን”ም እንደፍርሀት በመቁጠር እላያችን ላይ ይጸዳዱብናል፡፡ የመጸዳዳታቸው ውጤት የሆነው ክርፋትና ጥምባት ግን ፈጣሪን አስቆጥቶት ይሄውና … ቆይማ ብቻ፡፡ አሁን ምን አስቀባጠረኝ!
  • ሌላው ዜጋ በልዩ ልዩ ዘዴ ያፈራው ሀብት እንኳን ቢኖረው በሰቀቀንና በፍርሀት ተጀቡኖ በሁለተኛና ሦስተኛ ዜጋነት ነው የሚኖረው – ያሳዝናችኋል፡፡ አንገቱን ቀና አድርጎ እንደልቡ የሚኖረው ደንቆሮ ትግሬ ብቻ ነው፡፡ ዕድሜ ለወያኔዎች ሩቅ ተመልካች ትግሬ ሳይቀር ነገን በማሰብ አቀርቅሮ እንዲኖር የተገደደበት ሁኔታ ተፈጥሯል፡፡ ሌት ከቀን የሚዝናናው፣ በመኪናው ውስጥ በሚከፍተው የሙዚቃ ድለቃ በደረቅ ሌሊት ሕዝብን እንቅልፍ የሚነሳው፣ በየቡና ቤቱ እየዞረ ትግርኛ ካልተከፈተልኝ በማለት ሌላውን ዘፈን በነፍጠኛነት የሚፈርጀውና የሚያስፈራራው ጠግቦ እየዘለለ የሚገኘው ትግሬ ወያኔና አሽከሮቹ ናቸው፡፡ የሚገርመው ጠጪዉና ተዝናኙ ትግሬ ብቻ ነው ተብሎ በአዋጅ የተነገረ ይመስል በየመዝናኛውና በየምሽት ክበቡ የሚከፈተው ዘፈን ከሞላ ጎደል ትግርኛ ብቻ ነው፡፡ ትግርኛ ካልከፈታችሁ ቡና ቤታችሁ ይዘጋል የተባለ ይመስል አዳሜ ከገዢው ወገን ጋር የተዛመደ እየመሰለው የሚከፍተው ሙዚቃ ትግርኛ ብቻ የሚሆንበት አጋጣሚ ሞልቷል፤ ሁሉም ነገር የብሔር ተዋፅዖ በሚለው የወያኔ አስመሳይ ፍልስፍና እየተመራ(ከስልሳ የጦር ጀኔራል ስልሳውንም ትግሬ አድርገው ሲያበቁ እኮ ነው – አያስቁም? ድንቄም ተዋፅዖ!) ለምሳሌ የሞቀ ኦሮምኛ ተከፍቶ በምትጨፍርበት ሠርግ ላይ ሳታስበው ድንገት ትግርኛ ወይም ወላይትኛ ሊከፈት ይችላል – ያኔ የውዝዋዜ ሥልትህን በቅጽበት ትቀይርና በኩኑ ከማሆሙ ነባር ኢትዮጵያዊ ብሂል አንተም አለውድ በግድህ ሰሜነኛ ወይም ደቡብኛ ውዝዋዜውን ታስነካዋለህ – በአቅጣጫና በቁጥር ስያሜዎች አለቅን እኮ፡፡ አለዚያ “ይህን አይወድም፣ ይህን ይነቅፋል ወይ ይጠላል” በሚል ኢመደበኛ ግምገማ የሰው ዐይን ውስጥ ልትገባ ትችላለህ – በዚያም ሰበብ የምታጣው ነገር ሊኖር ይችላል፡፡ እስከዚህን የወረድን ሕዝብ ሆነናል – በዘፈን ምርጫ ሰውን መገምገም የሚዳዳባት ሀገር፡፡ እዚህ ላይ ትግርኛ መከፈቱ አስከፍቶኝ ሳይሆን ራስን ያለመሆን ጠባይ እየጎላ መምጣቱ ግን አስገርሞኝ ነው፡፡ በየትምህርት ቤቱማ ብታዩ ታሪኩ ብዙ ነው፡፡ በየቦታው የምትሰሙት ሙዚቃ አስመሳይነትን እንጂ እውነተኛ ፍላጎትንና ምርጫን አያመለክትም፡፡ ገበያን ለመሳብ ብቻ እንዴት የአንዲት ከተማ ቡና ቤቶች ተመሳሳይና የተሰለቹ ዘፈኖችን አንድን ወቅት እየጠበቁ (የስካርና የመዝናኛ) ይከፍታሉ? ወረተኝነት ከምን ጊዜውም በላይ እየተስፋፋ ነው፡፡ ነገ ደግሞ የሽናሻ መንግሥት ቢመጣ ቡና ቤቱ ሁሉ ሽናሽኛ ዘፈን እየለቀቀ ካለተዝናኙ ፍላጎት ሊያደነቁረው ነው ማለት ነው፡፡ ትንግርቱ ብዙ ነው፡፡ ይህን የምለው በጥራዝ ነጠቅ የማውቃት የሥነ ልቦና ትምህርት ግንዛቤየ እየታወሰችኝ ሰዎች የሚያደርጓቸውን ነገሮች ለምን፣ እንዴትና መቼ እንደሚያደርጉ ወይም እንደማያደርጉ የጫረብኝ አስጠሊታ ምስል ነው፡፡ ሰው ግን ምን ያህል አስመሳይ ፍጡር ነው!? ምን ነካን? ብንወርድ ብንወርድ እስከዚህ እንውረድ?
  • አዲስ አበባ ውስጥ ከሚዝመነመኑ ግሩም አውቶሞቢሎች ከአሥሩ በትንሹ ሰባቱ የትግሬዎች ናቸው ቢባል ስህተቱ ለኩነኔ አያደርስም፡፡ የንግድ መኪናውን ብትመለከትም እውነቱ ከዚህ ብዙም አይለይም፡፡ ትግሬ ግን ከኢትዮጵያ ሕዝብ አጠቃላይ ብዛት ግፋ ቢል 8 በመቶ ቢሆን ነው፡፡ የጥንቱን ስድስት በመቶውን አሁን እርሱት – አዲስ አበባ ላይ የሚርመሰመሰው ወያኔ ብቻውን ከአምስት በመቶ የሚያንስ አይመስለኝም – ለቁጥር ያለኝ ቀረቤታ እንደበውቀቱ ሥዩም እስከዚህም ቢሆንም፡፡ አማራው ቀንሷል – ትግሬው ጨምሯል፤ በምናውቃቸውም በማናውቃቸውም ምክንያቶች የተነሣ፡፡ ዘር ማብዣ ማዳበሪያ ወደትግራይ – ዘር ማምከኛ በስሪንጋ የሚሰጥ ብልቃጥ መርዝ ወደአማራ፡፡ ታሪክ ይፋዊ የምሥክርነት ቃሉን ሊሰጥ በቋፍ ላይ ነውና በትግስት እንጠብቅ፡፡ አለ ገና – ብዙ ነገር ይታያል፡፡ ዕድሜና ጤና መለመን ነው፡፡ አንድዬ የሚሳነው ነገር የለምና ያቆየን፡፡ የምመክራችሁ እንድትናደዱ ነው፤ ስትናደዱ ወደመፍትሔው ትጠጋላችሁ፡፡ አሪቬዴርቺ፡፡

 

↧

ወያኔ አንዳርጋቸው ያፈነበት እለት የሚረግምበት ቀን ሩቅ አይደለም!

$
0
0
Ginbot_7_Logo_Lህወሃት ጉጅሌ እንደማንኛውም አምባገነን ከፊት ከነበሩ አምባገነኖች ቅንጣት ትምህርት አልተማረም። ወያኔዎች በእብሪት የያዙት ስልጣንና ከህዝብ የዘረፉትን ንብረት የሚያጡት እየመሰላቸው በባነኑ ቁጥር የነጻነት አርበኞችን በማፈን በመግደልና በማሰቃየት ፍርሃታቸው የተወገደ ይመስላቸዋል።
ወያኔ የእኛ መሪና የኢትዮጵያ ህዝብ የነጻነት አርበኛ በሆነው አንዳርጋቸው ጽጌ ላይ ያካሄደው አፈና ከአፈናውም በሆላ በሚያደርሱበት አካላዊ ስቃይ ፍርሃታቸው የሚወገድ ወይም ስርአታቸው ከሞት የሚተርፍ መስሏቸው ከሆነ በእጅጉ ተሳስተዋል። አንዳርጋቸው ዛሬ በእጃቸው ሆኖ በነጻነት ይኖር ከነበረበት በበለጠ የሚለበልባቸው የውስጥ እግር እሳት ይሆናል።
አንዳርጋቸው ሰበአዊ ምቾቱንና ለራሱና ለቤተሰቡ መኖርን አቁሞ የኢትዮጵያን ህዝብ ነጻነት በህይወቱ ሊጋፈጥ ከቆረጠ ቆይቷል። እኛ የትግል ጓዶቹና ለህዝብ ነጻነት የቆሙ ሃይሎች ሁሉ አንዳርጋቸውን እናውቀዋለን። ወያኔ በአካሉ ላይ የለመደውን ስቃይ ጀምሮበታል፣ ከዚህ የበለጠም ጉዳት እንደሚያደርስበትም እናውቃለን። የአንዳርጋቸውን ታላቅ የነጻነት ሰውነትና ክብረ ህሊናውን፣ በአርበኝነቱ የሚሰማውን የኩራት ስሜቱን ለግፈኞች ያለውን ንቀትና መጸየፍ ሊለውጡ እንደማይችሉ አስረግጠን እናውቃለን።
አንዳርጋቸው እንደሁላችን ሰው ነውና በፈሪዎች በትር የሚደርስበት አካላዊ ስቃይ ግን ለህዝባችን የገባነውን ቃል ውሳኒያችንን እና አቋማችንን እንደብረት ያጠነክረዋል እንጂ አያላላውም።ይልቁንም በአንዳርጋቸው መታፈን ምክንያት ከመላ ሀገራችን በአለም ዙሪያ ከተበተነው ኢትዮጵያውያን እና ሌሎች የነሰታነት ሃይሎች የምንሰማውና እየሰማን ያለነው የሚያስገመግም ህብረ ድምጽ ከብረት የሚያጠነክር ሃይል ሆኖኗል።
አንዳርጋቸው የዘራው የነጻነት የአርበኝነት ዘር ከመብቀል አልፎ እየጎመራ በመሄድ ላይ ነው። አንዳርጋቸው ሺ አንዳርጋቸውን ተክቷል። ወያኔ አንዳርጋቸውን በማፈንና በእጁ አስገብቶ በራሱ መስኮት ቲቪ ስቃዩን እንግልቱን በማሳየት ሊያላምጠው የማይችል የብረት እንክብል ነው የነከሰው። ይህንንም ሳይውል ሳያድር ያየዋል፡፡
መላው ህዝባችን በእልህና በቁጭት ላይ ያለህ ወገናችን ና የሀገራችን የነሰታነትና የዴሞክራሲ ሃይሎች በሙሉ፡- በአንዳርጋቸው ላይ ወያኔ የፈጸመው የአሸባሪዎች ውንብድና በየአንዳንዳችን ላይ የተፈጸመ በደል ግፍ ነው።
ይህንን የሽብርና የውንብድና ስርአት ለማስወገድ አብረን ከመነሳት ውጪ አማራጪ የለንም። የልዩነታችንን አጥር አፍርሰን የወየኔን እድሜ እንድናሳጥር ግንቦት 7 ለሁላችንም ጥሪውን ያቀርባል።
አንድ ሆነን የአንዳርጋቸውን ስምና ምግባር እንሁን!
አንዳርጋቸው የዘራው እና እየጎመራ ያለው የአርበኝነት ንቅናቄ ተጠናክሮ ይቀጥላል። ወያኔ አንዳርጋቸውን ያፈነበት ቀን የሚረግምበት ጊዜ ከዚህ በኋላ ሩቅ አይሆንም፡፡
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!!!
source:G7
↧
↧

የአቶ አንዳርጋቸውን ቪዲዮ በጨረፍታ (ዮፍታሔ)

$
0
0

ዮፍታሔ

የሕወኀት አገዛዝ በዚህ ሳምንት የአቶ አንዳርጋቸውን ምስል በ“ኢትዮጵያ ቴለቪዥን” አሳይቶናል። ሕወኀት ይህን በማሳየት ምን ለማስተላለፍ እንደፈለገ በመጠኑ መዳሰስ መልካም ነው።

Andargachew Tsigeበመጀመሪያ ነገር አቶ አንዳርጋቸውን አግቶ መውሰዱን በተደጋጋሚ በቃል አቀባዮቹ ዲና ሙፍቲና ጌታቸው ረዳ አማካኝነት ሲያስተባብል የነበረ አገዛዝ ያስገደደው ወይም ቪዲዮውን በመልቀቅ ለማስተላለፍ የፈለገው ሳይኖር ይህን እንደማያደርግ መገመት ቀላል ነው። ሲያስተባብል ከአንድ ሳምንት በላይ የቆየ “መንግሥት” ወዲያው ደግሞ አቶ አንዳርጋቸው “በቁጥጥር ሥር” ውሎ ኢትዮጵያ መሆኑን በ“ጠቅላይ ሚኒስትሩ” በኩል በተናገረ በማግስቱ የአቶ አንዳርጋቸውን ምስል በቴለቪዥን አሳይቶናል።

ሕወኀት ይህን ለምን አደረገ? አራት ዋና ዋና ምክንያቶችን በቀላሉ ማቅረብ ይቻላል። ሌሎችም ከዚህ በፊት ተጠቅሰዋል። ወደፊት የምንደርስባቸውም ይኖራሉ።

የመጀመሪያው ሕዝቡና ተቃዋሚዎች በሚያዩት ነገር ተስፋ ቆርጠው እንዲያፈገፍጉ ለማድረግ፤ ሁለተኛ አቶ አንዳርጋቸውንና ከርሱ ጀርባ የተሰለፉትን ተቃዋሚዎች በሕዝብ ፊት አጣጥሎና አሳንሶ ለማሳየት፤ ሦስተኛው በተቃዋሚዎች መካከልና በሕዝቡና በተቃዋሚዎች መካከል ጥርጣሬ እንዲፈጠር ለማድረግ፤ አራተኛው ደግሞ በሕዝቡና በአገዛዙ ደጋፊዎች ሳይቀር እየተቀጣጠለ ያለውን የትግል ስሜት “ተመልከቱ ጨካኝ አይደለሁም፤ በአንዳርጋቸው ላይ ያደረስኩት ጉዳት የለም” በማለት ለማብረድ የሚሉ ናቸው። የዚህ ጽሑፍ ዓላማ የሕወኀትን ስሌት በመጠቆም ሁላችንም በነዚህ ወጥመዶች እንዳንገባ ለማሳሰብ ነው።

ቪዲዮውን በአጭሩ እንመልከተው። በ “Facebook” በመጀመሪያ የተለቀቀው ዜና (http://www.youtube.com/watch?v=oBxG4pTRNWA) የሚጀምረው የአቶ አንዳርጋቸውን ስም በመግደፍ ነው። የመጀመሪያዋን “አ” ፊደል በ “እ” በመቀየር “በጥብቅ ሲፈለግ የነበረው እንዳርጋቸው” ይለናል። መቸም ይህን ያህል “በጥብቅ ሲፈለግ የነበረ”፣ ከፖሊስ እስከፍርድቤቶች፣ ደኅንነትና ጦር ሠራዊት ድረስ አበጥሮ የሚያውቀውን ሰው ጋዜጠኛው ስሙን እንደማያውቅ ሆኖ ተሳስቶ ያነበዋል ማለት የማይታሰብ ነገር ነው። ዜናው በስቱዲዮ የሚሠራ እንደመሆኑ ቢሳሳት ኖሮ እንደገና ተስተካክሎ ሊቀረጽ የሚችልበትም እድል ነበረው። ያ ግን አልተደረገም። ምክንያቱ ሆን ብሎ የተደረገ እንደሆነ እንድንጠረጥር የሚያደርግ ነው። ይህ የተደረገው አቶ አንዳርጋቸውን ዝቅ ለማድረግም ብቻ አይደለም። እውነት ነው ይህን በማድረግ ስሙን አሉታዊ ትርጉም እንዲኖረው ለማድረግም ተሞክሯል። ነገር ግን ከዚህ ሁሉ በላይ ‘አንድአርጋቸው’ የሚለው ስም በሕዝቡ ዘንድ የአንድነት ስሜት በመፍጠር ትልቅ መነሣሣትን እየፈጠረ እንደሆነ አገዛዙ ተረድቷል። ጋዜጠኛው የአቶ አንዳርጋቸውን ስም በኋላ ሁለት ጊዜ አስተካክሎ ቢጠራውም አንዴ እንዳርጋቸው በኋላ አንዳርጋቸው እያለ መጥራቱ የአቶ አንዳርጋቸው ስም ‘በሚገባ እንኳን የማይታወቅ፤ ምንም ትርጉም የሌለው’ እንደሆነ ሲነግረን ነው። ይህን ስም አገዛዙ በቀጥታ በቴሌቪዥን እንዲጠራው ቢገደድም አስተካክሎ በመገናኛ ብዙኀን መጥራቱ የአንዳርጋቸው ስም በሕዝቡ ዘንድ የፈጠረውን ስሜት እንደመቀበልና እንደማበረታታት አድርጎ እንደተመለከተው በአስተማማኝ መገመት ይቻላል። ይልቁንም አብዛኛው አማርኛ ቋንቋን የሚረዳ ኢትዮጵያዊ በሚገኝበት በገጠራማው የአገራችን ክፍል ሕዝቡ አንድአርጋቸው የሚለውን ስም በሚሰማ ጊዜ የሚፈጠርበትን የጥቃትና የመነሣሣት ስሜት ሕወኀት ጠንቅቆ ያውቃል። ይህ ደግሞ አብዛኛው የኢትዮጵያ ገጠራማው ክፍል ከአገዛዙ መገናኛ ብዙኀን ውጪ ስለማይደርሰው ይህን ስም ከዚህ ቀደም አያውቀውም ከሚል ስሌት የመነጨ ነው። ስለዚህ ሆን ብሎ የአቶ አንዳርጋቸውን ስም አንዴ እንዳርጋቸው በሌላ ጊዜ አንዳርጋቸው ብሎ አደናጋሪ በማድረግ ከጠራ በኋላ በሌሎችም ተጨማሪ ‘የባዕድ’ ስሞች እንደሚጠራ ደግሞ ዘረዘረልን።

መቸም ሕወኀትን ለሚያውቅ እነዚህን ተጨማሪ የቅጽል ስሞች የዘረዘረው ለተጨማሪ መረጃ ነው ለማለት አይደፍርም። ነገር ግን መደበኛ የመረጃው አካል በማስመሰል ‘ስሙ አንዳርጋቸው የሚባል ቢሆንም ወገናችሁ እንዳይመስላችሁ እርሱ የፈረንጅ ስሞችን ጨምሮ በሌሎችም ስሞች የሚጠራ ከሀዲ ነው’ ለማለት ነው። “የሌሎች አገሮች ፓስፖርት መያዝ አያስጥልም” በማለት በዜናው የተጨመረውም ከማስፈራሪያ ሌላ “ዜግነታቸውን የቀየሩ” ለማለት እንደሚሆን መገመት ይቻላል። እንግዲህ ማጣጣልና ማንኳሰሱ ከዚህ ይጀምራል። አገዛዙ ያልተረዳው ግን የአንዳርጋቸውን ትክክለኛ ስም በመሸሽና በማሳሳት ሕወኀት በሕዝብ አንድነት ላይ ከፍተኛ ፍርኀት እንዳለው ቁልጭ አድርጎ ያሳየ መሆኑን ነው። ከዚህም በተጨማሪ የአንዳርጋቸው ትክክለኛ ስም ይህ ነገር ከመፈጠሩም አስቀድሞ በአገሪቱ እንደቋያ እሳት የተዛመተ መሆኑን ከሕዝቡ ጋር በቅርብ የሚኖሩት ካድሬዎች ያላደረሱት መሆኑን እንገነዘባለን።

ከዚያ በመቀጠል “በጥብቅ ሲፈለግ የነበረው” በማለት በመቶ ሺህ ጦር ሠራዊትና የጦር ጀት አለኝ የሚለው አገዛዝ የአቶ አንዳርጋቸው ድርጅት ምን ያህል የሚያስፈራው መሆኑን ራሱ በተዘዋዋሪ ሲመሰክር ይደመጣል። ምነው ይህ ድርጅት እንዲህ ሕወኀት የሚፈራውን ያህል ሆኖ በተገኘ ብለን የምንጓጓው በዚህም ምክንያት ነው።

በመቀጠል ‘የስለላ ድርጅቱ አስቀድሞ የአቶ አንዳርጋቸው የጉዞ ቀንና ፕሮግራም ደርሶት ከየመን ባለሥልጣናት ጋራ ባደረገው የተቀናጀ ሥራ’ በየመን ታግቶ “በዕለቱ” ወደኢትዮጵያ እንደተወሰደ ይናገራል። “አቶ አንዳርጋቸውን ለምን አገትከው?” እንጂ ‘በምን መረጃ ያዝከው?’ ብሎ አገዛዙን የጠየቀው ሳይኖር “የጉዞ ቀኑና ፕሮግራሙ አስቀድሞ ስለደረሰኝ” ያለበት ምክንያት የመረጃ ድርጅቱን ጀብዱ ብቻ ለመግለጽ ነው ማለት የዋህነት ነው። ከዚህ ይልቅ ‘የአቶ አንዳርጋቸውን የጉዞ መረጃ ማን አሳልፎ ሰጠ?’ በማለት በተቃዋሚዎች ላይ ሌሎች ተቃዋሚዎችና ሕዝቡ ጥርጣሬ እንዲፈጠርባቸው ለማድረግ እንደሆነ መገመት ይቻላል።

“በዕለቱ ወደኢትዮጵያ ተወስዷል” ያለበት ምክንያት ደግሞ እስካሁን የአቶ አንዳርጋቸው ድርጅት የሆነው ግንቦት ሰባት አቶ አንዳርጋቸው ከየመን ወደኢትዮጵያ ተላልፎ የተሰጠበትን ቀን በሚመለከት ሲያስተላልፈው የነበረውን “ውሸት ነው” ለማለትና ሕዝቡ ‘ለምን አቶ አንዳርጋቸው ከመጀመሪያው እንደታገተ አልተነገረንም?’ በሚል በድርጅቱ ላይ ቅሬታ እንዲፈጠርበት ለማድረግ ነው።  የግንቦት ሰባት ድርጅት እንደማንኛውም ድርጅት በየጊዜው እያስተካከላቸው የሚሄዱ አሠራሮች ሊኖሩት ቢችልም ከአቶ አንዳርጋቸው መታገት ጋራ በተያያዘ ያደረጋቸውን ውሳኔዎች በሚመለከት የምንወያይበት ጊዜ ላይ ያለመሆናችንን ልብ ማለት ያስፈልጋል። የዚህ ጽሑፍ አቅራቢ የግንቦት ሰባትም ሆነ የሌላ የፓለቲካ ድርጅት አባል አይደለም። ሆኖም ከአጠቃላይ ሂደቱ ግንቦት ሰባት የወሰዳቸው ውሳኔዎች ከመልካም ዝንባሌ መሆናቸውን ለመገመት ይቻላል የሚል እምነት አለው።

አቶ አንዳርጋቸው ወደሚታይበት ምስል እንሂድ።

በመጀመሪያ ነገር የአቶ አንዳርጋቸው ምስል፣ የአፉ እንቅስቃሴና ድምፁ አንድ ላይ አይሄድም። ይህን ለመረዳት ፊልሙን በቅርበት መመልከት ብቻ ይበቃል። ይህ ማለት ድምፁ ለብቻ ምስሉ ለብቻ ነው የተቀረጸው ማለት ነው። ይህም ብቻ አይደለም። ምስሉ ተቆራርጦ የተቀጣጠለ ነው። አቶ አንዳርጋቸው በጠቅላላ የሚታየው ለ 0፡42 ሰከንድ ሲሆን (ማለትም በጠቅላላው በዜናው ቪዲዮ ከደቂቃ 0፡57 – 1፡39) በዚህ ጊዜ ውስጥ ይህ እርሱ የሚታይበት ፊልም ቢያንስ 5 ጊዜ ተቆርጧል። የተቆረጠበት ቦታ በቅደምተከተል፦

  1. አቶ አንዳርጋቸው ሰው ጨብጦ እጁን ሙሉ ለሙሉ ከመሰብሰቡ በፊት (በዜናው ቪዲዮ 0፡59 ሰከንድ)
  2. ድምፁ  በእንግሊዝኛ “I was really really exhausted/ በጣም ደክሞኝ ነበር” ብሎ እንዳበቃ – በዜናው ቪዲዮ 1 ደቂቃ ከ20 ሰከንድ ላይ (1፡20)
  3. ድምፁ “ተረጋግቸ ያለሁበት ዓይነት ሁኔታ ነው ያለው” በማለት ላይ እያለ (1፡25)
  4. “ምንም ዓይነት despair (ተስፋ መቁረጥ) የለም” ካለ በኋላ (1፡34)
  5. “የመጨረሻ እርጋታና እረፍት ውስጥ ነው ያለሁት” ካለ በኋላ (1፡38)።

ከዚህበኋላአቶአንዳርጋቸውለአንድሰከንድፈገግሲልይታይናፊልሙያበቃል።

አቶ አንዳርጋቸው በዚህ ቪዲዮ ለ “ወንጀል ምርመራ” ቃል እየሰጠ ሳይሆን በሚገባ ከሚያውቀው ሰው ጋራ እየተጫወተ እንደተቀረጸ የሚያመለክት ፍንጭም ከዚሁ ጋራ ተያይዞ ይገኛል። ምክንያቱም አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ፈገግ ሲል የሚታይባት በመጨረሻ የተቀጠለችው የአንድ ሰከንድ ቪዲዮ ትክክለኛ ቦታ የሚመስለው በመጀመሪያ ከሚታየው ከእጅ መጨባበጡ በኋላ ነው። ነገር ግን አገዛዙ የሚያውቀውን ሰው እንደጨበጠ ተመልካቹ እንዳይጠረጥርና “አቶ አንዳርጋቸው ከወዳጁ ጋር የተጫወተውን እንደማስረጃ ቀርጾ አቀረበ” በሚል እንዳይወነጀልና “መረጃ”ውም ውድቅ እንዳይሆን የዚህን ጨካኝ ትዕይንት መጨረሻ ለማለስለስ ሲል ፈገግታውን ቆርጦ በመጨረሻ ወስዶታል። አገዛዙ የሚያቀርበው ነገር በሕዝብ ዘንድ አስቀያሚና የአገዛዙን ጭካኔ የሚያሳይ እንደሆነ ያውቃል። ያንን በተቻለ ለማለዘብ መግቢያውን በመጨባበጥ አድርጎ መዝጊያውንም በአቶ አንዳርጋቸው ፈገግታ አድርጎታል።

ዓላማው በ“ሰላምታ” ጀምሮ በአቶ አንዳርጋቸው ፈገግታ በመጨረስ ተመልካች ይህን መንፈስ በአእምሮው ይዞት ከትእይንቱ እንዲለይ ማድረግ ነው። ይህ ያነጣጠረው ደግሞ በሕዝቡና በአገዛዙ ደጋፊዎች ሳይቀር እየተቀጣጠለ ያለውን የትግል ስሜት “ተመልከቱ ጨካኝ አይደለሁም፤ በአንዳርጋቸው ላይ ያደረስኩት ጉዳት የለም። በሰላም ስንጨብጠው እርሱም ፈገግ ሲል እዩ” በማለት ለማብረድ መሆኑ አይጠረጠርም። ነገር ግን ይህ ቪዲዮ የተቀረጸው በአቶ አንዳርጋቸው ላይ ከፍ ያለ ድብደባና ጉዳት ከመድረሱ ቀደም ብሎ ባሉት ቀናት ሊሆንም የሚችል መሆኑን ልብ ማለት ያስፈልጋል። ይህን የሚያጠናክርልን የአቶ አንዳርጋቸው ጺም ነው። ከእንግሊዝ በተነሳበት ቀን ጺሙን ተላጭቶ ነበር ብለን ብንነሳ በፊልሙ ላይ የሚታየው የጺሙ እድገት ፊልሙ የተቀረጸበት ጊዜ ከእንግሊዝ በተነሣ ከ3 እስከ 5 ባሉት ቀናት ውስጥ እንደነበረ በቀላሉ እንድንገምት ያደርገናል። ያ ደግሞ ገና በመጀመሪያ በታገተበት ሰሞን መሆኑ ነው። ይህም ብቻ አይደለም። ይህ ሲጨብጠው የሚታየው ሰው “ወዳጅ”ነቱ ተቀባይነት እንዲኖረውና ተፈላጊውን ውጤት እንዲያስገኝ አንዳርጋቸውን ሊያገኘው የሚችለው ወደኢትዮጵያ በገባበት ሰሞን ነው። ከዚያ በኋላስ አቶ አንዳርጋቸው የት ነው ያለው? ከዚህ ቀደም በድብደባ ጉዳት ያደረሰበት አገዛዝ ዛሬስ ምን እያደረሰበት ነው? ማናችንም ይህን አናውቅም። ከዚህም በተጨማሪ ማሰቃያ መንገዶች ሁሉም በአካል ላይ በጉልህ የሚታዩ አይደሉም። እነዚህ ማሰቃያ መንገዶች አንዳንዶቹ ከድብደባም የሚብሱ እንደሆኑ በግልጽ ይታወቃል። አንድን ሰው በቪዲዮ ብቻ አይቶ ይህ የተፈጸመበት መሆኑንና ያለመሆኑን መናገር አይቻልም። ይህ ባልታወቀበት ሁኔታ ትግሉን አፋፍሞ ከመቀጠል በስተቀር ሌላ ምርጫ የለም።

አቶ አንዳርጋቸው ከሚያውቀው ሰው ጋር እየተነጋገረ እርሱ ሳያውቀው የተቀረጸ ስለመሆኑ ሌሎችንም ጠቋሚ ማስረጃዎች ማቅረብ ይቻላል። ከአቶ አንዳርጋቸው አጠቃላይ ንግግር መረዳት የሚቻለው ለመርማሪ ቀጥተኛ ጥያቄ መልስ የሚሰጥ ሳይሆን አስተዛዛኝ ለሆነ አስተያየት መልስ የሚሰጥ መሆኑን ነው። “ይህ ችግር መድረሱ ያሳዝናል! አይዞህ!” የሚል ዓይነት አስተያያት ተሰንዝሮለት “እኔ በጣም ደክሞኝ ነበር። እንዲህ መሆኑ ለበጎ ነው/ It is a blessing in disguise ምክንያቱም እረፍት እፈልጋለሁ። ምንም ቅሬታ የለኝም። በልቤ ውስጥ ተስፋ መቁረጥም የለም” በማለት ለዚህ ዓይነት አስተያየት ተገቢ የሆነ መልስ ሲሰጥ ነው የምናዳምጠው። ባለቤቱና ቤተሰቦቹ ንግግሩ እውነተኛ የአቶ አንዳርጋቸውን ተፈጥሮ የሚያመለክት ስለመሆኑ በአሜሪካ ድምፅ ሬድዮ ቀርበው የገለጹት ትክክለኛ የሆነበት ምክንያትም አቶ አንዳርጋቸው እየተቀረጸ መሆኑ ሳይገለጽለት ከሚያውቀው ሰው ጋር ይነገገር ስለነበረ ነው።

ፊልሙን በቅርበት ደግሞ እንየው። የፊልሙ ጥራት፣ የተቀረጸበት ቦታና ብርኃን የደበዘዘና የጨለመ መሆኑ አቶ አንዳርጋቸውን እንደ“ወንጀለኛ” እንዲታይ በተመልካቹ ዘንድ ድባብ ለመፍጠርና ጀግናውንና ከጀርባው የቆመውን ድርጅት በሕዝብ ዘንድ አሳንሶ ለማሳየት መሆኑ አይጠረጠርም። አቶ አንዳርጋቸው “የሆነው ነገር ለበጎ ነው/It is a blessing in disguise። እኔ በውስጤ ቅሬታ የለም። እረፍት ይሰማኛል” ሲል በማሳየት ሁሉም የያዘውን ትግል ተስፋ በመቁረጥ እንዲተው ማድረግ ሌላው የፊልሙ ዓላማ ነው። ነገር ግን እርሱ በትክክል ያስተላለፈው የተሟላ መልእክት “መታሰርህ ያሳዝናል!” ለሚል የ”ወዳጅ” አስተያየት “በጣም ደክሞኝ ስለነበር እንዳርፍ እድል አገኝበታለሁ። ተስፋ መቁረጥ ግን በልቤ ውስጥ የለም” የሚል ነው። ማንም ደጋግሞ ቪዲዮውን በዚህ መንፈስ ቢመለከተው ያለጥርጥር በተመሳሳይ መደምደሚያ ላይ ለመድረስ አይቸገርም። ለዚህም ነው ከዚህ በኋላ ምንም ዓይነት ከዚህ የተለየ “መረጃ” በአገዛዙ ቢቀርብልንም ልንቀበለው የማንችለው። ምክንያቱም አቶ አንዳርጋቸው በእንዲህ ዓይነት መጎሳቆል ውስጥ ሆኖ እንኳን “በልቤ ውስጥ ተስፋ መቁረጥ የለም” በማለት እቅጩን ተናግሯልና። ወደፊት ከዚህ የተለየ ነገር ብንመለከት ምን ያህል ጉዳት እንደደረሰበት አመልካችና ትግሉን እንደቋያ እሳት በስፋት የሚያቀጣጥለው ብቻ ነው የሚሆነው።

የአቶ አንዳርጋቸው ጺም ማደጉ ብቻ ሳይሆን በድምፁም ላይ ለውጥ እንዳለ መገንዘብ ይቻላል። ከዚህ ጺሙን የሚላጭበት ጊዜና ቦታ እንዳይኖረው ከመንፈግ ጀምረው ካደረጉት ድርጊትና በድምፁ ላይ ከምናስተውለው ለውጥ በነዚህ በመጀመሪያዎቹ ቀናት እንኳን ምን ያህል እንደተጎዳ መገመት ይቻላል። ይህም ብቻ አይደለም። እጁ ብቻ የሚታየውን ሰው በሚጨብጥበት ጊዜ የአቶ አንዳርጋቸውን የእጅ እንቅስቃሴ በቅርበት ማስተዋል ያስፈልጋል። ከላይ እንደተጠቀሰው ፊልሙ የተቆረጠው አቶ አንዳርጋቸው እጁን ሰብስቦ ከመጨረሱ በፊት ነው። ከዚህም በላይ በሚጨብጥበት ጊዜ ከተቀመጠበት ለመነሳት የፈለገ ቢመስልም በትንሹ እንኳን ብድግ ሊል አልቻለም። ለምን እጁን ሰብስቦ ሳይጨርስ ፊልሙ ተቆረጠ? በምስሉ ከሚታየው የሰውነቱ ክፍል በታች ምን ደርሶበታል? እነዚህንና የመሳሰሉትን ነገሮች ስናስብ የኢትዮጵያው አገዛዝ ጭካኔ አንድ ቀን እንኳን ሊያስተኛን አይገባም።

እንግዲህ አገዛዙ ያቀረበልን ዜና ይህን ይመስላል። ይህን ፊልም  ለ92 ሚሊዮን ሕዝብ እንደማስረጃ ማቅረብ ከውርደትም በላይ ውርደት ነው። ይሁን እንጂ ሕወኀት ይህን ፊልም በማሳየት “ማስረጃ” ነው ለማለት ከፈለገው ይልቅ በቪዲዮው ለሕዝቡ ሊያስተላልፈው የፈለገው የፕርሮፖጋንዳ መልእክት አመዝኖ ነው የሚታየው። ሊያስተላልፈው የፈለገው መልእክት ከላይ በአጭሩ እንደተገለጸው ግልጽ ከሆነ ሕዝቡና ተቃዋሚዎች እርሱ ያዘጋጀውን የፕሮፖጋንዳ ወጥመድ ሰባብረው በመሻገር ትግሉን ማጧጧፍ ይጠበቅባቸዋል።

በፓለቲካ ትግል የአቶ አንዳርጋቸው መታገትና መንገላታት የፈጠረውን የመሰለ ዕድል ብዙ ጊዜ የሚገኝ አይደለም። አንዳርጋቸው ጽጌ በሠራው አንጸባራቂ ሥራ ጀግንነቱን በታሪክ ምርጥ ከሆኑት የኢትዮጵያ የቁርጥ ቀን ልጆች መካከል አድርጓል። እርሱ መላ ሕይወቱን የሰጠበትን ትግል ከፍጻሜ በማድረስ ሁላችንም ድርሻችንን መወጣት ይጠበቅብናል። ስለዚህ እጅ ለእጅ ተያይዘን ወደፊት እንግፋ።

ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!

 

↧

አንድነት ፓርቲ ሰኔ 1 ቀን 2006 ዓ.ም በደ/ማርቆስ ያካሄደው ሰላማዊ ሰልፍ

↧

በሳውዲ አረቢያ –« ፀሎታችን በቤታችን » የኦርቶዶክ ተዋህዶ ምዕመናን ድምጽ

$
0
0

saudi orthox 2

saudi orthox
(Ethiopian Hagere ጅዳ በዋዲ )

በሳውዲ አረቢያ የምንኖር ኢትዮጵያውያን የኦርቶዶክስ ተዋህዶ እምንት ተከታይ ወገኖች «ጸሎታችን በቤታችን » በሚል መሪ ቃል የመጀመሪያውን ምእራፍ ትግል በድ ህረገጽ «ህ» ብለን መጀመራችን ግልጽ፡ነው። ይህን ትግላችንን ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር እይተደረገ ያለው ጥረት ተጠናክሮ ይቀጥላል። ይህ ሰላማዊ ትግላችን ብዥታ የፈጠረባቸው ጥቂት የመንግስት ካድሬዎች እና በራሳቸው መንፈሳዊ አዙሪት ተዘፍቀው የሚሰቃዩ ጽንፈኛ ግለስቦች ስለትግላችን መነሻ እና መዳረሻ ግራ ተጋብተው ሲወራጩ የስተዋላል ። በዚህም መስረት ጥያቄው ህጋዊ እና ሰላማዊ ለመሆኑ ግንዛቤ ለማስጨበጥ ያህል ጥቂት ለማለት ወደድን ።

ከሳውዲ አረቢያ በመቶ ኪሎ ሜተር ርቃ የምትገኝ ባህሬን በኢትዮጵያ ኮሚኒቲ ሰር የሚተዳደሩ 3 አበያተ ክርስቲያናት እንዳሉ አይተናል አድምጠናል ። በየመን «ሠነዓም» ኢትዮጵያውያኑ ምእመናን ባቀረቡት ጥያቄ ሂደቱ የቱንም ያህል ፈታኝ እና ተስፋ አስቆራጭ፡ እንደነብር ቢነገረም በስተመጨረሻ ውጤታማ ሆኖል ። ይህ በዚህ እንዳለ እንደተጠቀሱት ሃገራት የሳውዲ መንግስት በአንድ ቀን ጀምበር አወንታዊ ምላሽ ይሰጠናል የሚል እምነት ባይኖረንም የአንድ ሺህ ኪሎ ሜተር መንገድ በአንድ እርምጃ ይጀመራል እንዲሉ « ፀሎታችን በቤታችን » የትግላችን መነሻ መሆን እንዳለበት እናምናለን ። ለዚህም ሰላማዊ ሃይማኖታዊ የጸሎት ስፍራ ጥያቄ ስኬታማነት የዲፕሎማቶቻችን ትበበር ወሳኝ ሆኖ አጊተነዋል። በተለይ የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ምእመና ወገኖቻችን ተሰባስበው በደስታ ግዜ ምስጋና በሃዘን ግዜ የተማጽኖ ጸሎታቸውን ለፈጣሪያቸው የሚያደርሱበት እና ሃይማኖታዊ ግንዛቤዎቻቸውን የሚያዳብሩበት በጅዳ ቆንስላን ጽ/ቤት ግቢ እና ሪያድ የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ ፈጹም አማራጭ የምይገኝላቸው ቦታዎች መሆናቸው ይታመናል። ስለሆነም በግዜያዊነት የምንሰባሰብበት ቦታ እንዚህ ግቢዎች ውስጥ የስጠን ዘንድ ጥያቄ ማቅረብ መብት ነው። በሳውዲ አረቢያ የሚኖሩ ዲፕሎማቶቻችን የቱንም ያህል የእስልምና ህይማኖት ተከታይ ይሁኑ ጥያቄያችንን እስከተቀበሉ ድረስ ዲፕሎማቱ ባህሬን እና የመን ውስጥ ለዜጎቻቸው የጸሎት ቦታ ተጠበው ከኦርቶዶክስ ምዕመናን ህዝባቻቸው ጎን ቆመው ውጤት ካስመዘገቡት የመንግስት ዲፕሎማቶች ህገመንግስታዊ መንፈስ ውጭ ድብቅ አጀንዳ የሚያራምዱ ናቸው ብለን አናምነም ።

ሰለሆነም ሃገር እና ህዝብን ወክለው የተቀመጡ የመንግስት ዲፕሎማቶች እና በኤንባሲው ስር የሚገኙ ምቹ ተቋማት እያሉን ዜጎች በፀሎት ቦታ እጦት ድንበር አቋርጠን በህሬን ድረስ መሄድ አይጠበቅብንም። በአጭሩ ጥያቄያችን ጅዳ ፡ ሪያድ ጂዛን ከተማ ውስጥ የሚገኙ የኮሚኒቲ ማዕከላት ግዜያዊ የጸሎት ስፍራ እንዲዘጋጅለን እይተደረገ ያለ ተማጽኖ ነው ። ይህ “ ፀሎታችን በቤታችን” ጥያቄ ሳውዲ አረቢያ ውስጥ ያሉ የኦርቶዶክስ እምነት ተከታይ ወገኖቻችን የፀሎት ቦታ ጥያቄ አስመልክቶ በመሆኑ ሃገራችን ውስጥ ካለው ፖለቲካዊም ሆነ ሃይማኖታዊ ወቅታዊ ሁኔታዊች ጋር ምንም አይነት መስረታዊ ግንኙነት የለውም።። «ፀሎታችን በቤታችን » በሚል መረህ ቃል በመላ ሳውዲ አረቢያ የተጀመረው የኦርቶዶክስ ተዋህዶ እምነት ተከታይ ወገኖቻችን ጥያቄ የትኛውንም ሃይማኖት ሆነ የፖለቲካ ድርጀት መብት እና ነጻነት የማይነካ በመሆኑ አብዛኛው ኢትዮጵያዊ ወገኖቻችን ዘር ሃይማኖት ፖለቲካዊ አመለካከት ሳይለየው ድጋፋን በመግለጽ ላይ ይገኛሉ ።

ዛሬ «ፀሎታችን በቤታችን » ስንል በጅዳ ቆንስላ ጽ/ቤት ግቢ በሪያድ እና በጅዚን የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ ግቢ ውስጥ አነስተኛ የእምነት ቦታ ይፈቀድልን ነው ፡፤ይህ መሪ ቃል በኢትዮጵያን ሙስሊም ወገኖችን ዘንድ ተቀባይነትን ከማግኘቱም በላይ ከጎናችን ቆመው ለእቅዳቻችን መሳካት ከፍተኛ አስተዋጾ በማድረግ ላይ የገኛሉ፡፤ እኛ የኦርቶዶክስ እምነት ተከታይ ወገኖች በአንጻሩ ከሙስሊሙ ወንድሞቻችን ጎን ቆመን ለሃይማኖታቸው ነጻነት እያደረጉ ያለውን ሰላማዊ ትገል በተለያየ መንገድ ድጋፍ ፋችንን በመግለጽ ላይ መሆናችን የማይታበል ሃቅ ነው። ይህ በአንድነት ላይ የተመስረተው ጽናታችን ያስበረገጋቸው ጥቂት ዲፕሎማቶች እና በራስቸው የፈጠራ መንፈሳዊ አዙሪት የስከሩ ጽፈኛ ግለሰቦች በህዝበ ሙስሊሙ እና የኦርቶዶክስ እምነት ተከታይ ወገኖች መሃል እየተሽሎከለኩ መርዘኛ አስተሳሰባቸውን ሲረጩ ይስተዋላል፡፡፤ ይህ በፍጹም ተቀባይ ነት የሌለው እና ህዝባችን በጋራ መከላከል የሚገባው ሴጣናዊ አስተሳሰብ ነው ፡፤ ሁለቱ ሃይማኖቶች ማለት የኦርቶዶክ እና የእስልምና ሃይማኖት ምዕመናን የማይነጣጠሉ አንዱ የሌለውን በደል እና ጭቆና ማየትን የማይሻ ለዘመናት ተከባብረው እና ተቻችለው የኖሩ ወደፊትም የሚኖሩ ህዝቦች ለመሆናቸው አብነት መጥቀስ አያሻም። ዛሬም ኢትዮጵያውያኑ የኦርቶዶክስ ምዕመናን ሳውዲ አረቢያ ያሉብንን የጸሎት ቦታ ጥያቄ ለመፍታት በምናደርገው እቅስቃሴ ግራ ሳይጋቡ ድጋፋቸውን እየገለጹ ያሉ ወገኖቻችንን ስናመሰገን እነዚህ ወገኖች እስከ መጨረሻው ከጎናችን ቆመው አጋርነታቸውን እንደሚገልጹ አንጠራጠረም ። ትግሉ ተጀምሯል !! ክርስቲያን ተስፋ አይቆርጠም ! « ፀሎታችን በቤታችን» ግዜያዊ አሰባሪ ኮሚቴ ጅዳ ሳውዲ አረቢያ

↧

የአቶ አንዳርጋቸው ፅጌ ጉዳይ ከሰኔ 16 እስከ ሐምሌ 4

$
0
0
Andargachew Tsige.jpg2

አቶ አንዳርጋቸው ፅጌ

የግንቦት ሰባት የፍትሕ፣ የነፃነትና የዴሞክራሲ ንቅናቄ ዋና ፀሐፊ የአቶ አንዳርጋቸው ፅጌ የመን ላይ ተይዞ ለኢትዮጵያ መሰጠት በስፋት እያነጋገረ ነው፡፡

የግንቦት ሰባት የፍትሕ፣ የነፃነትና የዴሞክራሲ ንቅናቄ ዋና ፀሐፊ የአቶ አንዳርጋቸው ፅጌ የመን ላይ ተይዞ ለኢትዮጵያ መሰጠት በስፋት እያነጋገረ ነው፡፡

የሚመሩት ንቅናቄ ግንቦት ሰባት ተከታታይ መግለጫዎችን አውጥቷል፤ ዜጋ የሆኑበት የእንግሊዝ መንግሥት፣ የሰብዓዊ መብቶች ተሟጋች ድርጅቱ ሂዩማን ራይትስ ዋች፣ የግንቦት ሰባት አጋሮችና ሌሎችም ድርጅቶች የየመንን አድራጎት አውግዘዋል፤ የየራሣቸውን ጥያቄዎች አሰምተዋል፡፡

የኢትዮጵያ መንግሥትም ሽብርተኛ መሪ መያዙንና በኢትዮጵያ ሕግ መሠረት የሚገባውን እንደሚያገኝ ገልጿል፡፡

ከላይ የሚገኘው የድምፅ ፋይል የእስካሁኑን ሂደቶች ማጠቃለያ፣ የአቶ አንዳርጋቸው ፅጌን ባለቤት ወ/ሮ የምሥራች ኃይለማርያም እና የወንድማቸውን የአቶ ብዙነህ ፅጌን ሃሣቦች እንዲሁም የተለያዩ ወገኖችን አስተያየቶችና የኢትዮጵያን መንግሥት ምላሽ ይዟል፤ ያዳምጡት፡፡

http://amharic.voanews.com/flashaudio.html

አቶ ሺመልስ ለራዲዮ ፍራንስ አንተርናሲዮናል በሰጡት መግለጫ ላይ የተጠናቀረውን ዘገባና ቃለ-ምልልሣቸውን ለማዳመጥ ከታች የተቀመጠውን ማገናኛ ተጭነው ይከተሉ፡፡

http://www.english.rfi.fr/africa/20140709-extradited-opposition-leader-face-consequences-despite-british-nationality-says-ethi

ግንቦት ሰባት የፍትሕ የነፃነትና የዴሞክራሲ ንቅናቄን መግለጫዎች ለማንበብ ከታች የተቀመጠውን ማገናኛ ይጫኑና ይከተሉ፡፡

http://www.ginbot7.org/2014/07/10/ፋሽስታዊ-ፕሮፖጋንዳው-እና-ምላሻችን!/

የአቶ አንዳርጋቸው ፅጌን መያዝ የሚናገረውን የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ዜናና የአቶ አንዳርጋቸውን ቃል ለማየት ከታች የተቀመጠውን ማገናኛ ይጫኑና ይከተሉ፡፡

http://www.youtube.com/watch?v=LkxKkd1kk8g

 

↧
↧

ቴዲ አፍሮ በሚኒሶታ የተሳካ የሙዚቃ ኮንሰርት አቀረበ፤ 38ኛ ዓመት የልደት በዓሉን በዚሁ መድረክ አከበረ

$
0
0


(ዘ-ሐበሻ) በጉጉት ሲጠበቅ የነበረውና በብዙዎች ዘንድ መነጋገሪያ የነበረው የዝነኛው ድምጻዊ ቴዲ አፍሮ የሙዚቃ ኮንሰርት በተሳካ ሁኔታ ተጠናቀቀ። በሚኒሶታ ግዛት በሚኒያፖሊስ ዳውን ታውን በተካሄደውና ብዙ ሕዝብ በታደመው በዚህ ወደ ፍቅር ጉዞ ኮንሰር ላይ ቴዲ ድንቅ ብቃቱን ዳግም አሳይቶ ለሕዝቡም ጥሩ ምሽት እንዲያሳልፍ ምክንያት ሆኗል።

በሚኒያፖሊስ ከተማ እየተደረገ ባለው የኦል ስታር ጨዋታዎች የተነሳ ወደ ቴዲ አፍሮ ኮንሰርት የሚመጣው ሕዝብ የመኪና ፓርኪንግ ለማግኘት የተቸገረ ከመሆኑም በላይ አንዳንድ ሰዎች በዚህ የተነሳ ኮንሰርቱን ሳይታደሙ ሊቀሩ እንደቻሉ ዘ-ሐበሻ አረጋግጣለች።

በዚህ ትልቅ የሙዚቃ ኮንሰርት ላይ የቴዲ አፍሮ የሙዚቃ ባንድ አቡጊዳ፤ ቴዲ ሊዘፍን መድረክ ላይ ሲወጣ ዘፈኑን ስልት በመለወጥ ወደ”ሃፒ በርዝ ደይ” ሙዚቃ በመቀየር ቴዲ አፍሮን ሰርፕራይዝ አድርገውታል። በመድረኩ ላይ ከሕዝቡ ጋር 38ኛ ዓመቱ የተከበረለት ቴዲ ከሕዝብ ከፍተኛ የሆነ ፍቅር የተቸረው ሲሆን እርሱም ለአድናቂዎቹ “ከሁለት ዓመት በኋላ ባላቴና መባሌ ይቆማል” ሲል ተናግሯል።

ቴዲ አፍሮ በዚህ የሙዚቃ ኮንሰርቱ 2 አዳዲስ ነጠላ ዜማዎችን ለሕዝብ ያደረሰ ሲሆን ኮንሰርቱ በጣም ድንቅ እንደነበር የታደሙት ሰዎች ለዘ-ሐበሻ አስተያየታቸውን ሰጥተውናል።

ቪድዮዎች ይመልከቱ

Teddy Afro Rocks Minnesota (Video)

↧

ቆይታ ከአንዳርጋቸው ጽጌ እህት ጋር! “ለአንዳርጋቸው አታልቅሱ!” እስከዳር ጽጌ

↧

የአዲስ አበባ የመሬት ቅርጫ (መስፍን ወልደ ማርያም)

$
0
0

መስፍን ወልደ ማርያም
ሚያዝያ 2006

Prof. Mesfin

መስፍን ወልደ ማርያም

ዮሐንስ ታደሰ አካ የሚባል ወጣት ስደተኛ  የተስፋው ነጸብራቅ  የሚል መጽሐፍ እአአ በ2013 በጀርመን አገር አሳትሞአል፤ ሳይፈራ ሀሳቡን የሚገልጽ በመሆኑ ሳይሆን አይቀርም በታወቀው ሦስተኛ ፖሊስ ጣቢያና በቃሊቲም ታስሮ ነበር፤ እሱ እንደሚለው

‹‹በአዲስ አበባ ማዘጋጃ ቤት የመሬት አስተዳደር ባለሥልጣን ውስጥ … የመሬት መሀንዲስ›› ተብሎ በ2000 ዓ.ም. ተቀጠረ፤ ከተቀጠረ በኋላ በቦዘኔነት ደመወዝ እየበላ ቆየ፤ ቀይቶ እንደተገነዘበው ‹‹… ለካስ እንኳንስ የእያንዳንዱ ሠራተኛ የሥራ ድርሻ ተለይቶ ሊታወቅ የመሥሪያ ቤቱም ሥራ አይታወቅም፤ መሥሪያ ቤቱም ሥራውን አያውቅም፤ የመሥሪያ ቤቱም ሃላፊዎች መሥሪያ ቤቱን አያውቁትም፤ ጉድ በል አዲስ አበባ! የምናወራው ስለዝነኛው አዲስ አበባ ከተማ መስተዳድር ነው።›› (ገ. 19)

 

ስለፋይሎች ስቃይ፣ ውጣ-ውረድ፣ መተሻሸት፣ መጎሳቆል ዮሐንስ ያለርኅራኄ ይተርካል፤ የእነዚህ ፋይሎች መሰቃየትና መጎሳቆል በአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎች ላይ የሚደርሰውን ሥርዓት የያዘ ግፍ የሚያንጸባርቅ ነው፤ በግፍ ሲሰቃዩ ያየው ፋይሎችን ብቻ ሳይሆን ሰዎችንም ነው፤ በሦስተኛ ፖሊስ ጣቢያና በቃሊቲ ያየውን በብዙ ሰዎች ላይ የተፈጸመውን መከራና ስቃይ ይናገራል፤ ኢትዮጵያን ‹‹ባለማጥፋት ከጥፋተኛነት የማይድኑበት አገር›› ያደርጋታል፤ ኢሕአዴግንም ውሸታም ከማለት ይልቅ ‹‹የሌለ ማንነት አላብሶ ይሾምሃል፤ የሌለ ማንነት አላብሶ ይሽርሃል፤›› በማለት ይገልጸዋል።

ለእኔ መጽሐፉ የያዘው ሌላ ጥሩ መረጃ ስለአዲስ አበባ የቅርጫ መሬት ሰንጠረዥ ነው፤ ብዙ ሰው መሬት እንደተነጠቀ፣ ብዙ ሰው በድንገት የሰፋፊ መሬት ባለቤት እንደሆነ፣ ብዙ ሰው ቤቱ እየፈረሰበት ከነበረበት ደሀነት የባሰ ደሀነት ውስጥ እንደገባ፣ ብዙ ሰው ከመናጢ ደሀነት ተነሥቶ መሬት አልበቃ ብሎት ወደሰማይ ወደመንጠራራት እንደደረሰ እናያለን፤ እንሰማለን፤ ነገር ግን ይህንን የአዲስ አበባን ሕዝብና መሬት እየቆፈረ ግልብጥብጥ እያደረገ፣ የነበረውን የሚያጠፋና የሚጠፋውን የሚክብ ሁነት መጠኑን አናውቅም፤ መጽሐፉ ውስጥ ባለው ሰንጠረዥ ላይ የሚታየው በቅርጫ የተደለደለው መሬት ‹‹ለመኖሪያ ግንባታዎች ብቻ›› የተሰጠውን እንጂ ‹‹ለሆቴልና ለቅይጥ አገልግሎቶች›› የተሰጡትን አይጨምርም፤ አንዱ ሲከዳ ደግሞ ያንን መረጃም እናገኘዋለን።

ዮሐንስ ለመጽሐፉ የተስፋው ነጸብራቅ የሚል ስም የሰጠው ለምን እንደሆነ ግን በቅጡ አልገባኝም፤ በመጽሐፉ ውስጥ ከተገለጸው ግፍና መከራ ውስጥ ተስፋ የሚባል ነገር ጭላንጭሉም የለም፤ ጠንቋዩ እንዳለው ቢሆንምን ጨምረንበት የተስፋው ተካፋይ መሆን እንችላለን።

በአጠቃላይ ለመኖሪያ ቤት ቅርጫ ባለመብት ሆነው በሰንጠረዡ ውስጥ የገቡት አንድ መቶ ሠላሳ ስምንት ሰዎች/ኩባንያዎች ብቻ ናቸው፤ በአጠቃላይ ያገኙት መሬት ከስድስት ሚልዮን ካሬ ሜትር በላይ ነው፤ አንድ መቶ ሠላሳ ስምንቱ ተረካቢዎች ወይም ተጠቃሚዎች ያገኙት በአማካይ እያንዳንዳቸው 43748 (አርባ ሦስት ሺህ ሰባት መቶ አርባ ስምንት) ካሬ ሜትር መሬት ነው።

ያገኙት፣ ወይም ተረካቢዎቹ፣ ወይም ተጠቃሚዎቹ በአንድ በኩል፤ አስረካቢዎቹ ወይም ያጡት ወይም የተጎዱት በሌላ በኩል ስንት እንደሆኑ በእርግጠኛነት አናውቅም፤ ግን መገመት የምንችል ይመስለኛል፤ ለእያንዳንዱ ለተፈናቀለ ደሀ አንድ መቶ ካሬ ሜትር ለመኖሪያ ብናስብ እያንዳንዱ የቅርጫው ተሳታፊ 437 (አራት መቶ ሠላሳ ሰባት ያህል ደሀዎችን በአማካይ አስነቅሎአል ማለት ነው፤ ለቅርጫ የገባውን መሬት ለማግኘት ከስድሳ ሺህ በላይ ደሀዎች ከነቤተሰቦቻቸው ለባሰ ደሀነት ተዳርገዋል ማለት ነው፤ ስድሳ ሺህ ማለት ከሦስት መቶ ሺህ በላይ ግለሰቦችን ያካትታል፤ ደባሎችን ስንጨምርበት ቁጥሩ በጣም ከፍ ይላል፤ እንግዲህ 138 (አንድ መቶ ሠላሳ ስምንት) ቤተሰቦችን ወይም 690 (ስድስት መቶ ዘጠና) ግለሰቦችን ለመጥቀም ከሦስት መቶ ሺህ በላይ ሰዎች ተጎድተዋል ማለት ነው።

ይህ ሲሆን ስንት ቁም-ነገር ነው የተፋለሰው? የዜጎች ያለስጋት የመኖር ነጻነት፣ የዜጎች በአገራቸው ሀብት ላይ ያላቸው እኩልነት፣ ደሀዎችና ደካማዎች የሆኑ ዜጎች ሊኖራቸው የሚገባ የኑሮ ዋስትና፣ ይህ ሁሉ ነጻነትና መብት በግላጭ ሲገፈፍበትና  ሲያለቅስ አቤት የሚልበት ዳኛ ማጣት ደግሞ ዋናው ግፍ ነው።

የአዲስ አበባ የመሬት ቅርጫ የተከናወነበት ጊዜም የመሬት አስረካቢዎችንና የመሬቱ ተረካቢዎችን ያልተፈጸመ ታሪክ ያመለክታል፤ ለመኖሪያ ተብሎ ለቅርጫ ከቀረበው መሬት 41.3 ከመቶ የሚሆነው በ1998 ዓ.ም. የተከናወነ ሲሆን 16.2 የሚሆነው በ1997 ዓ.ም. የሆነ ነው፤ የቀረው ከ1997 በፊትና ከ1988 በኋላ የተቀራመቱት ነው፤ ከዚህ በፊት አንዲህ ሰፊ የሆነ የብዙ ዜጎች መፈናቀልና የጥቂቶች ተጠቃሚ መሆን የታየው በኢጣልያ ወረራ ጊዜ ነው፤ አንዳጋጣሚ አንዳንድ ቤቶች በኢጣልያ ወረራ ጊዜና አሁንም ባለቤቶቻቸው መጎዳታቸው የሚያስደንቅ ነው።

የቅምያና የዝርፊያ ጊዜ እንዳለ ሁሉ የፍትሕና የማስተካከያ ጊዜ አለ፤ ደሀዎችን ለሚያደኸዩ ጊዜ እንዳለ ሁሉ ዘራፊዎችን ሙልጭ ለሚያወጡ ጊዜ አለ፤ ሰሎሞን ለሁሉም ጊዜ አለ ብሏልና!

↧
Viewing all 15006 articles
Browse latest View live