Quantcast
Channel: Ethiopian News | ዘ-ሐበሻ | Latest News Provider | News For All
Viewing all 15006 articles
Browse latest View live

የግብፅ ኮፕቲክ ኦርቶዶክስ ቤ/ክርስቲያን ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ቴዎድሮስ ሁለተኛ በኖርዌይ የሶስት ቀናት ጉብኝት አደረጉ

$
0
0

ኖርዌይን በመጎብኘት የመጀመርያ የኮፕት ፓትርያሪክ ናቸው
የጉዳያችን ልዩ ጥንቅር -ፎቶዎች ይዘናል (Gudayachn Exclusive)

የግብፅ ኮፕቲክ ኦርቶዶክስ ቤ/ክርስቲያን ፓትርያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ቴዎድሮስ ሁለተኛ በኖርዌይ ከ ሰኔ 12-14/2006 ዓም ባደረጉት ጉብኝት ከፍተኛ አቀባበል በኖርዌይ መንግስት የተደረገላቸው ሲሆን ከኖርዌይ ንጉስ ሃራልድ፣ከጠቅላይ ሚንስትር ወ/ሮ አርና ሱልበርግ እና ከውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ብረንደ ጋር ተወያይተዋል።

የፓትርያርኩ ጉብኝት  በግብፅ ባለው ፖለቲካዊ እና ሃይማኖታዊ ጉዳይ ላይ ለመወያየት የኖርዌይ ቤተክርስቲያን ባደረገችላቸው ጥሪ ምክንያት መሆኑን ለማወቅ ተችሏል።በመካከለኛው ምስራቅ ውስጥ ካሉት አብያተክርስቲያናት በርካታ ምዕመናንን ያላት የግብፅ ኮፕቲክ ቤተክርስቲያን በብዙ ወከባ እና ፈተና ላይ መሆኗን የኖርዌይ መንግስት እና የሃይማኖት ድርጅቶች እንደሚረዱ በተወካዮቻቸው አማካይነት ለፓትርያርኩ እና ለልዑካኑ ገልፀዋል።

በአፀፋው ፓትርያርኩ በግብፅ ያለውን ተጨባጭ ሁኔታ ማስረዳታቸው እና በተለይ አርብ ሰኔ 13/2006 ዓም በኖርዌይ ከሚገኙ የተለያዩ የክርስቲያናዊ ድርጅቶች ጋር ልዩ ውይይት አድርገዋል።በፓትርያርኩ ለውይይት የቀረበው የመውያያ አርዕስት ”በወቅታዊው የግብፅ ፖለቲካዊ እና ሃይማኖታዊ ሁኔታዎች ውስጥ የኮፕቲክ ቤተክርስቲያን የገጠሟት ተግዳሮቶች” (”Dilemmas and challenges for the Coptic church in the current political and religious situation in Egypt”) የሚል ሲሆን ፅሁፉ የግብፅ ክርስቲያኖችን መፃኢ ፈተና እና ከዓለም ዓቀፉ ማህበረሰብ እና ከኖርዌይ የሚጠበቀውን ድጋፍ ያመላከተ እንደሆነ ለማወቅ ተችሏል። ፓትርያርክ ቴዎድሮስ ሁለተኛ ከሁለት ዓመት በፊት ህዳር ወር ላይ በተደረገ ሲመት ከእዚህ ዓለም በሞት የተለዩትን አቡነ ሺኖዳን ተክተው የተሾሙ መሆናቸው ይታወቃል።

ከእዚህ በታች ፓትርያርክ ቴዎድሮስ ሁለተኛ በኖርዌይ ባደረጉት ጉብኝት በኦስሎ ”ዱም ሺርኬ” ቅዳሜ ሰኔ 14/2006 ዓም ባደረጉት የፀሎተ-ቅዳሴ ስነ-ስርዓት በጉዳያችን ጡመራ የተነሱ ፎቶውዎችን ነው። 

Abune Tewodros 9 Abune Tewodros 1 Aba+Tewodros+10 (1)

 


ፀረ ሙስና ኮሚሽን የምድር ባቡር የድሬዳዋ ኃላፊዎችን በቁጥጥር ሥር አዋለ

$
0
0

112የፌደራሉ ፀረ ሙስና ኮሚሽን የድሬዳዋ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት የቀድሞ የኢትዮ-ጂቡቲ ምድር ባቡር ኩባንያ የድሬዳዋ ተጠሪንና አራት ሌሎች የአመራር አባላትን፣ በሙስና ወንጀል በመጠርጠር በቁጥጥር ሥር አዋለ፡፡

ከድሬዳዋ በተገኘ መረጃ መሠረት ሰኔ 10 ቀን 2006 ዓ.ም. ጀምሮ በፖሊስ ቁጥጥር ሥር የዋሉት የቀድሞው ዋና ተጠሪ አቶ አየለ ወልደ ዮሐንስ፣ የሐዲድና የሕንፃ ኃላፊ አቶ ፋንታሁን ገበየሁ፣ የሳብ ተሳሳብ ኃላፊ የነበሩት አቶ ታደሰ ኃይለ ማርያም፣ የአኬሌ ወርክሾፕ ኃላፊ አቶ ፍቅረ ማርያም አበባየሁና የንግድና ትራንስፖርት ተጠሪ የነበሩት አቶ ደርብ ጉደታ መሆናቸው ታውቋል፡፡

አቶ አየለን ጨምሮ አምስቱም ተጠርጣሪዎች በድሬዳዋ ከተማ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ሰኔ 12 ቀን 2006 ዓ.ም. ቀርበዋል፡፡ የኮሚሽኑ ዓቃቤ ሕግ ሥልጣንን ያላግባብ በመጠቀም፣ የመንግሥትን ይዞታ ለግለሰቦች በሕገወጥ መንገድ በማከራየትና የመንግሥት የግዢ ሥርዓት ሳይጠብቁ ግዢ በመፈጸም ክስ መመሥረቱን ለማወቅ ተችሏል፡፡

ባለፈው ሚያዝያ ወር በተመሳሳይ የድሬዳዋ ፖሊስና የፀረ ሙስና ኮሚሽን ፖሊስ በጋራ በመሆን የኢትዮ ጂቡቲ ምድር ባቡር ዋና ሥራ አስፈጻሚ የነበሩትን አቶ ጣዕመ ተኪኤን፣ ጉቦ በመቀበል ወንጀል በድሬዳዋ ከተማ ውስጥ ባረፉበት ሆቴል በቁጥጥር ሥራ ማዋላቸውን መዘገባችን ይታወሳል፡፡

Source: Ethiopian Reporter

ከአሥር ወራት በላይ የኤሌክትሪክ ኃይል ያጡ የፍቼ ነዋሪዎች ሰላማዊ ሠልፍ ሊወጡ ነው

$
0
0

-ካህናትና የነዋሪዎች ተወካዮች ዋና መሥሪያ ቤቱን ተማፀኑ819f5b6eb52350a170986a3670177bfb_Lላለፉት አሥር ወራት ከኤሌክትሪክ ኃይል ወደ ኩራዝ ብርሃን ለመመለስ ተገደናል ያሉ በኦሮሚያ ክልል የፍቼ ከተማና አካባቢው ነዋሪዎች፣ ሰኔ 16 ቀን 2006 ዓ.ም. ሰላማዊ ሠልፍ ለማድረግ ለከተማው አስተዳደር ጥያቄ ማቅረባቸውን አስታወቁ፡፡

ነዋሪዎቹ ሠልፍ እንደሚወጡ የከተማውን አስተዳደር መጠየቃቸውን የገለጹት፣ ነዋሪዎቹን ወክለውና የከተማውን የኦርቶዶክስ ተዋህዶ እምነት አባቶችን ልብሰ ተክህኖ በመልበስና ሌሎች የሃይማኖት ተወካዮች እንደእምነታቸው ለብሰው፣ ፒያሳ በሚገኘው የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የደንበኞች አገልግሎት መስጫ ተገኝተው ቅሬታቸውን ባሰሙበት ወቅት ነው፡፡

የፍቼ ከተማ ነዋሪዎች ላለፉት አሥር ወራት የኤሌክትሪክ ኃይል አጥተው መክረማቸውን የመሥሪያ ቤቱ ቅርንጫፍ መሥሪያ ቤት እማኝ መሆኑን የሚናገሩት ነዋሪዎቹ፣ ከፍቼ እስከ አዲስ አበባ ከተማ ያሉትን ቢሮዎች ቢያዳርሱም፣ አንዱ ወደ ሌላኛው ቢሮ እንዲሄዱ ከመንገር ባለፈ የፈየዱላቸው እንደሌለ አስረድተዋል፡፡ ብሶታቸው እየባሰ በመምጣቱና ከመንግሥት አንድ ቁርጥ ያለ ምላሽ ማግኘት እንዳለባቸው በማመናቸው፣ ሁሉንም የከተማውን ነዋሪዎች በመወከል ከ25 የሚበልጡ ተወካዮች በዋናው መሥሪያ ቤት ተገኝተው ቅሬታቸውን አሰምተዋል፡፡

‹‹ጥያቄያችን የኤሌክትሪክ ኃይል ብቻ ነው፤›› ያሉት ነዋሪዎቹ፣ ለብዙ ጊዜያት በኤሌክትሪክ ኃይል መጠቀም የለመዱ ነዋሪዎች እንደገና ወደኋላ በመመለስ በኩራዝና በማገዶ እንዲጠቀሙ ማድረግ ተገቢ አለመሆኑንና በተለይ በዕድሜ የገፉ እናቶችና ጨቅላ ሕፃናት ከፍተኛ ጉዳት እየደረሰባቸው መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ በመሆኑም የሚመለከተው የመንግሥት አካል መፍትሔ እንዲሰጣቸው ጠይቀዋል፡፡ በመሥሪያ ቤቱ የተለመደው ምላሽ ‹‹ትራንስፎርመር አልተገዛምና የለም›› መሆኑ ማብቃት ስላለበት መንግሥት ትኩረት ሰጥቶ ሊሠራ እንደሚገባም ጠይቀዋል፡፡

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አገልግሎት መስጫ መሥሪያ ቤት አንድ ኃላፊ በሰጡት ምላሽ፣ ‹‹ሁለት ሰው ይበቃ ነበር፣ ብዙ በመሆናችሁ ቅር ብሎኛል፡፡ እኛ እናንተን ማገልገል እንጂ ሌላ ዓላማ የለንም፡፡ ከእኛ ቅርንጫፍ መሥሪያ ቤት አንድ ሰውና ከእናንተ አንድ ሰው ይበቃ ነበር፡፡ ወይም በወረቀት ደብዳቤ ብትጽፉም በቂ ነበር፡፡ ሁለተኛ እንዳይደገም፤›› በማለት ምላሽ ሰጥተዋል፡፡ ችግሩን አጣርተው መፍትሔ ምላሽ እንደሚሰጡም ተናግረዋል፡፡

እንደ ፍቼ ነዋሪዎች ለአሥር ወራት የቆየው የኤሌክትሪክ ኃይል መጥፋት ችግር ባያጋጥምም፣ ከአምስት ቀናት እስከ አንድ ወር ድረስ የኃይል መጥፋት ችግር የሚያጋጥማቸው የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎችም በተለያየ መንገድ እሮሮ እያሰሙ ነው፡፡ አዲስ አበባ ከተማ በሁሉም ክፍላተ ከተሞች በተደጋጋሚ የኤሌክትሪክ ኃይል እየጠፋ እንደሆነ ራሱ መሥሪያ ቤቱ ምስክር እንደሚሆን፣ እንደማይጠራጠሩ ስድስት ኪሎ የካቲት 12 ሆስፒታል አካባቢ ነዋሪ የሆኑት ወ/ሮ ትዕግሥት በላቸው በእርግጠኝነት ይናገራሉ፡፡

ወ/ሮ ትዕግሥት የኤሌክትሪክ ኃይል በተከታታይ ለአራት ቀናት ካልጠፋ ‹‹የዓባይ ግድብ ደረሰ መሰለኝ፣ ተመስገን ያለምንም ችግር ጨለማ ሳይውጠን ከረምን፤›› እስከማለት መደረሱን ተናግረዋል፡፡

ከዳግማዊ ምኒልክ ሆስፒታል እስከ ሾላ ገበያ ድረስ ያሉ ነዋሪዎች ለዘጠኝ ተከታታይ ቀናት የኤሌክትሪክ ኃይል በማጣታቸው ‹‹የዓለም ዋንጫ ለኛ ሲባል ሊደገም ነው አሉ…›› እያሉ በችግሩ ላይ ማሾፍ መጀመራቸውንም ወ/ሮ ትዕግሥት አንድ ዘመዳቸውን ለመጠየቅ በሄዱበት ወቅት መታዘባቸውን ጠቁመዋል፡፡

እንደነ ወ/ሮ ትዕግሥት አካባቢ ሁሉ በሽሮሜዳ፣ በፒያሳ፣ በሜክሲኮ፣ በቃሊቲ፣ በአቃቂ፣ በጎተራ፣ በቦሌ፣ በኮተቤ፣ በአስኮ፣ በላፍቶ፣ በልደታና በሌሎች አካባቢዎች የኤሌክትሪክ ጉዳይ አነጋጋሪ ብቻ ሳይሆን ጥያቄም እያስነሳ መሆኑን ነዋሪዎች እየገለጹ ነው፡፡

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ኮርፖሬሽን ለሁለት መከፈሉ ይፋ ከተደረገ አንድ ዓመት ሳይሞላው እየተፈጠሩ ያሉት ችግሮች፣ ነዋሪዎችን ግራ እንዳጋቡ የሚገልጹ አንዳንድ አስተያየት ሰጪዎች፣ የኤሌክትሪክ ኃይል የሚቋረጠው ‹‹ኢትዮጵያ ውስጥ ነው ወይስ ከእኛ ከገዙት ጁቡቲና ሱዳንም?›› በማለት ጥያቄ እያሰኑ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

ኮርፖሬሽኑ ሁለት ቦታ ተከፍሎ የሠራተኞች ምደባ እንደ አዲስ መደረጉ ለችግሩ ዋና ምክንያት ሳይሆን እንዳልቀረ የሚናገሩት አስተያየት ሰጪዎቹ፣ በተለይ የአገልግሎት ዘርፉን የተረከበው የህንዱ ኩባንያ ሥራውን በአግባቡ እየተወጣው አለመሆኑን ጠቁመዋል፡፡

ነባር ሠራተኞች ሥራውን በደንብ የሚያውቁት ቢሆንም፣ በተደረገው አዲስ የመዋቅር ለውጥ ድልድል ሳያኮርፉ እንዳልቀሩ የሚናገሩት አስተያየት ሰጪዎች፣ የሚመለከተው አካል ይኼንን ሁኔታ በደንብ አጥንቶ አስቸኳይ መፍትሔ ካልሰጠው፣ ችግሩ የከፋና ውጤቱም አደገኛ እንደሚሆን አስጠንቅቀዋል፡፡ የአገልግሎት ዘርፉን ከሚመራው የህንዱ ኩባንያ ጋር የሥርጭት ዘርፉን በኃላፊነት የሚመሩት የሥርጭት ሥራ አስፈጻሚ አቶ ቢትወደድ ገብረ አሊፍን ለማነጋገር ቢሞከርም ስልካቸውን ስለማያነሱ አልተሳካም፡፡

Source: Ethiopian Reporter

አንድነት ፓርቲ በሀዋሳ ሊያደርገው የነበረው ሰልፍ አመራሮችንና አባላትን በማሰር ከተማዋን በፀጥታ ኃይሎች በመውረር ተደናቀፈ

$
0
0
በዛሬው ዕለት በአዋሳ ከተማ አንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) በሀዋሳ ከተማ ሊያካሂድ የነበረውን ሰላማዊ ሰልፍ አስመልክቶ በቅስቀሳ ላይ የነበሩ የፓርቲው አባላት ከሐሙስ ዕለት ጀምሮ እስከ ትላንት ድረስ ከ30 በላይ በፖሊስ የታሰሩ ሲሆን የሲአን የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ለገሰ ላንቃሞ ለምን ይታሰራሉ ብለው በመጠየቃቸው እሳቸውንም አስረው ከምሽቱ 3፡30 ለቀዋቸዋል፡፡ በቅስቀሳው ወቅት ወረቀቶች የተበተኑ በመሆኑ ህዝብ በነቂስ ሊወጣ እንደሚችል ስጋት ያደረባቸው የደህዴን ካድሬዎች ትላንት ማታ ከምሽቱ 3፡00 ሰዓት ተጨማሪ 7 የአንድነት የሀዋሳ አመራሮችና አባሎች በቁጥጥር ስር አውለዋል፡፡ የደቡብ ክልል የደህዴን ካድሬዎች ከተለቀቁ ነገ ሰልፉን ከማድረግ ወደኋላ አይሉም በሚል ለሁለት ተከፍለው ሲሟገቱ ማምሸታቸውንና አቶ መንድሙ ወታንጎ የተባሉት የደህንነት ኃላፊ መፈታት የለባቸውም መፍታት እንኳን ካለብን የሰልፉ ሰዓት ካለፈ በኋላ ነው በማለታቸው በእስር ቤት እንዲያድሩ መወሰኑና በዛሬውም ዕለት የሀዋሳ ከተማ በፀጥታ ኃይሎች ከፍተኛ ጥበቃ ሥር መሆኗን የፍኖተ ነፃነት ምንጮች ገልፀዋል፡፡

10478183_742597102465708_4057302345624676295_n

1

 

2

1511   102503 1511 10417631_742597265799025_630295793578646597_n 10492

ከጅማ ዩኒቨርሲቲ ተይዘው በቂሊንጦና ቃሊቲ የታሰሩት ፈቲያና ያሲን በወህኒ ቤት ተሞሸሩ

$
0
0

ከዳዊት ሰለሞን

የሙስሊሞችን ሰላማዊ የተቃውሞ እንቅስቃሴ ተከትሎ ብዛት ያላቸው የእምነቱ ተከታዩች ለእስራት መዳረጋቸው አይዘነጋም፡፡ፈቲያና ያሲንም ይማሩበት ከነበረው ጅማ ዩኒቨርስቲ ተይዘው በቂሊንጦና ቃሊቲ ወህኒ ቤቶች ከታሰሩ አንድ ዓመት ተቆጥሯል፡፡

(ጋዜጠኛ ዳዊት ሰለሞን ቤተሰቦቻቸውን ቃለምልልስ ሲያደርግ)

(ጋዜጠኛ ዳዊት ሰለሞን ቤተሰቦቻቸውን ቃለምልልስ ሲያደርግ)


ወህኒ የተከረቸመባቸው ሁለቱ ወጣቶች በያዝነው ክረምት በጋብቻ ለመጣመር (ኒካህ ለማሰር) እቅድ ነበራቸው፡፡የወህኒ በሮች ቢቆለፍባቸውም ፣ወዳጅ ዘመዶቻቸው ተሰባስበው ድል ባለ ሰርግ ለመጋባት ባይቻላቸውም ልባቸው አንድ በመሆኑ ቀን የቀጠሩላት ጊዜ እንድታልፋቸው አልፈቀዱም፡፡
ኬክ አስጋግረው ፈቲያን እንኳን ደስ አለሽ ለማለት ዛሬ ከቀኑ ስድስት ሰዓት ቃሊቲ የተገኙ ጓደኞቿን፣ቤተሰቦቿንና ታናሽ ወንድሟን የማግኘት ዕድል አጋጥሞኝ ነበር፡፡ለወትሮው ፈቲያን ለመጠየቅ በቃሊቲ የሚፈቀደው ከ6፡00 እስከ 6፡30 ነበር ፡፡
ቃሊቲ በር ላይ ለፍተሻ የተመደቡ ፖሊሶች የፈቲያን ጎብኚዎች ‹‹ቀለበት ይዛችሁ እንደመጣችሁ መረጃ ደርሶናል›› በማለት ጠንከር ያለ ፍተሻ ሲያካሄዱባቸውም ተመልክቻለሁ፡፡

ኬክ ይዘው ፈቲያ ጋር እንደደረሱ የሰርግ ዘፈን ጓደኞቿና ቤተሰቦቿ መዝፈን መጀመራቸው ግን ፖሊሶቹን አላስደሰተም እናም ከአምስት ደቂቃ በላይ ሳያገኟት ግቢውን ለቀው እንዲወጡ ተደርገዋል፡፡

‹‹ምን ተሰማሽ››የፈቲያ የልጅነት ጓደኛዋ የሆነች ወጣትን ጠየቅኳት‹‹በዚህ ቀን እንኳን እንድናግራት አልፈቀዱልንም፡፡ፈቲያ ግን አንድም ቀን ስለሆነው ነገር ስታማርር ሰምቼያት አላውቅም፡፡የእርሷ የመንፈስ ጥንካሬ እኔንና መሰሎቼን እንድንበረታ ያደርገናል››ብላለች፡፡
በተመሳሳይ መልኩ በዛሬው ዕለት ያሲንን በቂሊንጦ በመጎብኘት ወዳጆቹ ‹‹እንኳን ደስ አለህ››ማለታቸውን ሰምቼያለሁ፡፡

ቴዲ አፍሮ በሲያትል የተሳካ የሙዚቃ ኮንሰርት አደረገ፣ በሳንሆዜና በሚኒሶታ ይቀጥላል

$
0
0

(ዘ-ሐበሻ) “ወደ ፍቅር ጉዞ” በሚል መርህ ቴዲ አፍሮ በሰሜና አሜሪካ የሚያደርገው የሙዚቃ ኮንሰርት ትናንት በሲያትል ዋሽንግተን ተጀመረ። በሺህዎች የሚቆጠሩ የቴዲ አፍሮ አፍቃሪዎች ይህን ኮንሰርት የታደሙት ሲሆን ቴዲም ሲያስደስታቸው እንዳመሸ ከሲያትል ለዘ-ሐበሻ የደረሰው መረጃ ያመለክታል።
teddy afro seattle 2

teddy afro seattle
ከሥራ ፈቃድ ጋር በተያያዘ በዋሽንግተን ዲሲና በዳላስ ቴክሳስ ይደረግ የነበረው ኮንሰርት መሠረዙ የሚታወስ ሲሆን ባለፈው ሳምንት መጀመሪያ ላይ ድምጻዊው የሥራ ፈቃዱን በማግኘቱ ትናንት በሲያትል የደመቀ ምሽት አሳልፏል።

ቴዲ ወደ ፍቅር ጉዞ በሚል የጀመረው የሙዚቃ ኮንሰርት ጁላይ 3 በሳንሆዜ የኢትዮጵያ ስፖርት ፌስቲቫል ላይ የሚቀርብ ሲሆን ጁላይ 4 ለአሜሪካ የነፃነት ቀን ከአፍሪካ ድምጻውያን መካከል ተመርጦ ይዘፍናል።

ከዚያ ቀጥሎ ጁላይ 12 በሚኒሶታ የሚያደርገው ዝግጅት በጉጉት እየተጠበቀ እንደሚገኝ ዘ-ሐበሻ ከደረሷት መረጃዎች ለማረጋገጥ ችላለች።

ቴዲ አፍሮ የፍቅር ጉዞውን ወደሚኒሶታ ጁላይ 12 ካደረገ በኋላ በሰሜን አሜሪካና በካናዳ የተለያዩ ዝግጅቶችን የሚያቀርብ ሲሆን ከዚያም ወደ አውሮፓ እንደሚያቀና ይጠበቃል። ዘ-ሐበሻ እንደደረሳት መረጃ ከሆነ በላስቬጋስ ለኢትዮጵያ አዲስ አመት ሥራውን እንደሚያቀርብም ነው።

የኢትዮጵያው ሙዚቃ ንጉሥ ጥላሁን ገሰሰ እግርን ተከትሎ በኢትዮጵያ ሕዝብ ልብ ውስጥ የነገሠው ቴዲ አፍሮ በቅርቡ አንድ ነጠላ ዜማ እንደሚለቅና ሙሉ የአልበም ዝግጅቱን እንደጨረሰም የዘ-ሐበሻ ምንጮች ጠቁመዋል።
ቴዲ በሲያትል

የሚበሉና የማይበሉ ምግቦች – ለአስም ህመምተኞች

$
0
0

 ዶ/ር ብርሃኔ ረዳኢ

asthma       በዚህ የክረምት ወራት መግቢያ ወቅት የአስም ህመም የሚቀሰቀስባቸው ሰዎች በርካታ ናቸው፡፡ ህመሙ ከፍተኛ ደረጃ የደረሰባቸው ደግሞ ወቅትና ጊዜ ሳይጠብቅ መተንፈስ እስኪሳናቸው ድረስ ለሰአታት እያንቋረሩ ሲያስሉ ማየት ለቤተሰብና ወዳጅ አስጨናቂ ነው፡፡ በዚህ ጊዜ ያድናል የተባለ መድኃኒት፣ ምግብና የባህል ህክምና ሁሉ ይሞከራል፡፡ በተለይ በዚህ የጭንቀት ሰዓት ይፈውሳል ተብሎ ሚሰጠው ምግብ ሊያባብስ እንደሚችል የዘርፉ ባለሙያዎች ይገልፃሉ፡፡ ለአስም ህመምተኞች የሚሆኑ እና የማይሆኑ ተብለው የተለዩ ምግቦች የሚከተሉት ናቸው፡፡

 አፕል

በእንግሊዝ የተካሄደ አንድ ጥናት በሳምንት ከ2 እስከ 5 አፕል የሚመገቡ ሰዎች አስማቸው የመቀስቀሱ መጠን በ32% ዝቅ ብሎ መገኘቱን ገልጧል፡፡ በፍሬው ውስጥ የሚገኘው Flovonoids የተሰኘው ንጥረ ነገር ለዚህ ውጤት መገኘት አስተዋፅኦ ሳይኖረው እንደማይቀርም ተገምቷል፡፡

ካሮት

በሰውነት ወደ ቫይታሚን ኤ የሚቀየረውን ቤታካሮቲን የተሰኘ አንቲኦክሲደንት በካሮት ውስጥ በብዛት ይገኛል፡፡ በቤታካሮቲን ላይ እየተካሄዱ ያሉ ቅድመ ጥናቶች ንጥረ ነገሩ በእንቅስቃሴ የሚነሳ አስምን ለመቆጣጠር ያስችላል፡፡ ካሮት ለአይን ጤንነት እና ለበሽታ መከላከል አቅም ከሚሰጠው ጥቅም በተጨማሪ ከልብ፣ ከካንሰርና ከመርሳት (አልዛይመር) በሽታዎች ይጠብቃል፡፡ ቤታካሮቲን በስኳር ድንች እና በቃርያ ውስጥም ይገኛል፡፡

ቡና

በየጊዜው ቡናን የተመለከቱ መረጃዎች ይወጣሉ፡፡ ይጠቅማል ይጎዳል የሚሉ፡፡ አስምን በተመለከተ ግን ቡና ጥቅሙ ያመዝናል፡፡ በቡና ላይ የተደረጉ ሰባት ጥናቶችን የመረመረ አንድ የሳይንቲስቶች ቡድን ቡና ከተጠጣ በኋላ ባሉ አራት ሰዓታት የአየር ቧንቧዎች በተሻለ ሁኔታ እንዲሰሩ እንደሚያደርግ ደርሼበታለሁ ብሏል፡፡ ኒዮርክ በሚገኘው የሌኖክስ ሂል ሆስፒታል የውስጥ ደዌ ስፔሻሊስት የሆኑት ዶ/ር ሮበርት ግራሃም ‹‹ካፌይን አየር መተላለፍን ያሻሽላል፡፡ ጥቁር ሻይም ጠቃሚ ነው፡፡›› ሲሉ የቡና አስተዋፅኦ የማይናቅ መሆኑን ይገልፃሉ፡፡

እንቁላል   

በአንዳንድ ሰዎች ላይ ሽፍታ በመፍጠር እንቁላል አለርጂ ለመቀስቀስ ምክንያት ነው፡፡ አስም ሊነሳ ሊያደርግም ይችላል፡፡ የእንቁላል አለርጂ በተለይ በህፃናት ላይ የሚታይ ሲሆን እያደጉ ሲሄዱ ብዙዎችን ይተዋቸዋል፡፡ ልጅዎ የእንቁላል አለርጂ ካለበት(በሃኪም ተመርምሮ መታወቅ ይገባዋል) እንቁላልና በእንቁላል የተሰሩ ምግቦችን እንዳይመገብ ያድርጉ፡፡ ብናኝ በሚበዛባቸው፣ እምክ እምክ በሚሸቱ ቢሮዎችና ቤቶች የሚሰሩና የሚኖሩ ሰዎች የአስም ስሜት እንዳይዳብርባቸው ሲባል እንቁላልን አዘውትረው እንዲመገቡ አይመከርም፡፡

ተልባ     

ተልባ በኦሜጋ-3 አሲዶችና በማግኒዥየም የበለጸገ ነው፡፡ አንዳንድ ጥናቶች በዓሳ ውስጥም በከፍተኛ መጠን የሚገኘው ኦሜጋ-3 ለአስም ጥሩ ነው ለማለት የሚያስችል ቀዳሚ ውጤት እንዳገኙ ይገልፃሉ፡፡

ማግኒዥየም በመተንፈሻ አካላት ዙርያ ያሉ ጡንቻዎችን በማላላት አተነፋፈስን ቀላል ከማድረጉም በላይ ትቦዎቹ ክፍት ሆነው እንዲቆዩ እንደሚያደርግም የውስጥ ደዌ ስፔሻሊስቱ ዶ/ር ግርሃም ይናገራሉ፡፡

ነጭ ሽንኩርት

ለበርካታ ዘመናት የፈዋሽ ምግቦችን ዝርዝር በቁንጮነት ሲመራ ኖሯል፡፡ አሁንም ተወዳዳሪ አልባ መሆኑን የተለያዩ ጥናቶች እየመሰከሩለት ነው፡፡ ለአስም ፈዋሽ እንደሆነም ዶ/ር ግርሃም ይመሰክራሉ፡፡ እ.ኤ.አ በ2009 የተካሄደ አንድ ጥናት ግን ካንሰር አማጪ ፍሪ ራዲካልሶችን የሚያጠፋው allicin የተሰኘ ንጥረ ነገር በነጭ ሽንኩርት እንደይገኝ ገልጾ ነበር፡፡

ወተት

አንዳንድ መረጃዎች ወተትና ውጤቶቹ አስምን እንደሚቀሰቅሱ ይገልፃሉ፡፡ ጥቂት ሰዎች ደግሞ የወተት አለርጂ አለባቸው፡፡ ይህ አለርጂ ለመተንፈስ መቸገር፣ ሳል እና ሌሎች የመተንፈሻ አካል ችግሮችን ይፈጥራል፡፡

በሌላ በኩል ደግሞ ወተት የቫታሚን ዲ ምርጥ መገኛ በመሆኑ የአስም ምልክቶችን ለማለዘብ ይረዳል፡፡ ኤክስፐርቶች አስምን ለመቆጣጠር ዋናው መላ አለርጂ ቀስቃሾችን በይፋ ማወቁ ላይ ነው ይላሉ፡፡

ኦቾሎኒ

በአንዳንድ ሰዎች ላይ አደገኛ አለርጂ ይቀሰቅሳል፡፡ በሌሎች ላይ ደግሞ የአስም አለርጂ ይፈጥራል፡፡ አንድ ጥናት የኦቾሎኒ አለርጂ ያለባቸው ሕፃናት ከሌሎች በተለየ በአስም የመጠቃ እድላቸው ከፍተኛ መሆኑ ተገልጧል፡፡

በርካታ አስም ያለባቸው ለኦቾሎኒ አለርጂ የሆኑ ህፃናት በሳር፣ በአረም፣ በድመቶች፣ በአቧራ፣ በአበባ ብናኝ እና በመሳሰሉት አስማቸው ሊቀሰቅስ ይችላል፡፡ ብዙዎቹም ሆስፒታል በመተኛት ህክምና ለመከታተል ይገደዳሉ፡፡

ጨው

አየር መተላለፊያ ትቦዎችን ያጠባል፣ በሰውነት ውስጥ የውሃ እጥረት እንዲፈጠር ያደርጋል፡፡ ‹‹የአስም ምልክቶች የሚታያቸው ሰዎች ዝቅተኛ ጨው መመገብ ይኖርባቸዋል›› ይላሉ ዶ/ር ግራሃም፡፡

ወይን

በርካታ ጥናቶች በውስጡ የሚገኘው sulfites የተሰኘ ንጥረ ነገር አስም እንዲቀሰቀስ እንደያደርግ ፅፈዋል፡፡ ሌሎች ጥናቶችም ራሱ አልኮሉ ወይም ሌላ ግብአት የፈጠረው ሊሆን ይችላል ቢሉም ወይን አስምን ይቀሰቅሳል በሚለው ላይ ግን ተስማምተዋል፡፡

አንዳንድ ጥናቶች ደግሞ ቀይ ወይን መጠጣት የአስምን ምልክቶች ቀንሶ አግኝተናል ብለዋል፡፡

አቮካዶ 

ለሰውነት በጣም አስፈላጊ ከሚባሉት አንቲኦክሲደንቶች ውስጥ Glutathione የተሰኘው አቮካዶ ውስጥ ይገኛል፡፡ በርካታ ኤክስፐርቶች የአንቲኦክሲደንቶች ጥቅም ሰፊና ዘርፈ ብዙ እንደሆነ ይገልፃሉ፡፡

ዋነኛ ተግባራቸውም ሌሎችን ከጉዳት መከላከልና ተበላሽተው ወደ ፍሪ ራዲካልነት የተለወጡ ሌሎችን ማወገድ ነው

ምንጭ፡- አዲስ ጉዳይ መፅሄት

Source- www.mahederetena.com/amharic/archives/1765

 

 

 

 

Health: ይልቅ የኮክን (Peach)ጥቅም ልንገርሽ * ለዕድሜ፤ ለዓይን፤ ለቆዳ ውበትና ሌሎችም አስፈላጊሽ ነው

$
0
0

peaches-pile
በሊሊ ሞገስ

 ኮክ (Peach) መገኛው ቻይና ነው፡፡ አሌክሳንደር ዘግሬት ከቻይና ወደ ግሪክ እንዳመጣውም ይነገራል፡፡ ለአሜሪካ ያስተዋወቁት ደግመኮ ስፔናዊያን ናቸው፡፡ በዛፍ ላይ የሚበቅለው ኮክ ሶስት የዕድገት ደረጃዎች አሉት፡፡ የመጀመሪያው እስከ 50ኛው ቀን ይዘልቃል፤ ይህ ወቅት ተክሉ በፍጥነት የሚያድግበት ጊዜ ነው፡፡ በሁለተኛው ደረጃ በተክሉ ውስጠኛ ክፍል (ጠጠሩ) መጠንከር ይጀምራል፡፡ ነገር ግን የዕድገት ደረጃው ዝግ ያለ ነው፡፡ ‹‹final sweet›› ተብሎ በሚጠራው የመጨረሻ የእድገት ደረጃ ተክሉ ተወዳጅ ቀለሙን ይይዛል፡፡ ውሃ ይቋጥራል፣ ስኳር የሚይዘውም በዚህ ወቅት ነው፡፡

የጤና ጠቀሜታዎቹ

ዕድሜ ቀጥል ነው

ቻይናዊያን የኮክን የጤና ጠቀሜታዎች የተረዱት 10ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ነበር፡፡ ጠጠሩን ለህክምና ተግባር ከማዋላቸው ባለፈ ኮክን ‹‹longevity peach›› ብለው ይጠሩታል- ዕድሜ ቀጥሉ ኮክ እንደማለት፡፡ ዘመናዊው የህክምና ሳይንስ ጥንታዊ ቻይናዊያን ኮክን ለህክምና ያውሉበት የነበረው ዘዴ እና የሚሰጠው ጠቀሜታ ትክክል እንደሆነ መስክሯል፡፡

በቫይታሚን እና ሚኒራሎች የበለፀገ ነው

ኮክ በበርካታ ቫይታሚኖች እና ሚኖራሎች የበለፀገ ቢሆንም ዕድሜ ማራዘሙ የሚታወቀው ግን በውስጡ የያዘው ፖታሲየም ነው፡፡ ከኮክ ከፍተኛ መጠን ያለው ፖታሲየም ይገኛል፡፡ በሰውነታችን ውስጥ የፖታሲየም እጥረት ከተከሰተ ድካም፣ ጭንቀት፣ የጡንቻ መድከም፣ የቆዳ ችግሮች፣ ደካማ የማስታወስ አቅም፣ የደም ግፊት፣ የተለያዩ የልብ ህመሞች እና በጆሮዎች ውስጥ የመርገብገብ ድምፅ መሰማት ዋና ዋና ምልክቶቹ ናቸው፡፡ የሆድ ዕቃ ህመሞች፣ ተቅማጥና ከፍተኛ ላብ የሚታይባቸው ሰዎች የፖታሲየም እጥረት ሊያጋጥማቸውና ከላይ በተጠቀሱት ህመሞች በቀላሉ ሊጋለጡ ይችላሉ፡፡

ቤታ ካሮቲን- ቫይታሚን ኤ

ኮክን ለጤና ተስማሚ ካደረጉት ንጥረ ነገሮች ውስጥ ቤታ ካሮቲን አንዱ ነው፡፡ ሰውነታችን ቤታ ካሮቲንን ወደ ቫይታሚን ኤ ይቀይረዋል፡፡ ቫይታሚን ኤ ደግሞ ለበርካታ የሰውነታችን ስራዎች አስፈላጊ ነው፡፡ በቅርብ ጊዜ ለንባብ የበቃ አንድ ጥናት በሰውነታቸው ውስጥ ከፍተኛ የቫይታሚን ኤ ያላቸው ሰዎች የዓይን ሞራ የመጠቃት ዕድላቸው ዝቅተኛ ነው ብሏል፡፡ ሌሎች ጥናቶች ደግሞ ከፍተኛ የቫይታሚን ኤ መጠን ሰውነት ውስጥ ሲገኝ አደገኛ የሳንባ ህመምን ሊያስወግድ እንደሚችል በአይጦች ላይ የተደረጉ ጥናቶች አሳይተዋል ይላሉ፡፡

የዓይንን ጤንነት ይጠብቃል

Lycopene እና Lutein ተብለው የሚጠሩ መደባቸው ከ ካሮቲኖች የሆኑ ንጥረ ነገሮች፣ ልክ እንደ ቤታ ካሮቲን ኮክ የምናውቀው ቀለም እንዲኖው ይረዳሉ፡፡ በነዚህ ሁለት ንጥረ ነገሮች ላይ የተካሄዱ በርካታ ጥናቶች የሁለቱ በበቂ መጠን መገኘት ከዕድሜ ጋር በተያያዘ የሚከሰትን የአይን መድከም፣ ካንሰርን እና የልብ በሽታዎችን ይከላከላል፡፡

በፋይበር የበለፀገ ነው

ኮክ ከፍተኛ የፋይበበር ይዞታ አለው፡፡ ሁለት አይነት ፋይበሮች ናቸው ያሉት… በውሃ የሚሟሟውና የማይሟሟው፡፡ የሚሟሟው ለልብ ጤንነት ጠቃሚ ነው፡፡ ምክንያቱም ውሃ ስለማይዝ ነው፣ ይህ ደግሞ ድርቀትን ይከላከላል፡፡ ይህም አንጀት ውስጥ ተከማችተው የሚገኙ ተረፈ ምርቶችን ለማስወገድ ያስችላል፡፡ በዚህ የተነሳም የአንጀት ካንሰር እንዳይከሰት ይረዳል፡፡ የአንጀት ግድግዳ መጽዳት ሰውነታችን ንጥረ ነገሮችን በተገቢው ሁኔታ እንዲጠቀም ከማስቻሉም በላይ መርዛማ ንጥረ ነገሮችን ያስወግዳል፡፡ በውሃ የማይሟሟው ፋይበርም ቢሆን ጠቀሜታ አለው… የኮሌስትሮል መጠንን ዝቅ ያደርጋል፡፡

የቫይታሚን ሲ ዋነኛ መገኛ ብርቱኳን እንደሆነ የማያውቅ ሰው ጥቂት ነው፡፡ ኮክም በቫይታሚን የበለፀገ ነው፡፡ ቫይታሚን ሲ በሽታ ተከላካይ ሲሆን የበሽታ መከላከል አቅምን በማጎልበት ካንሰርን ይከላከላል፡፡ በተጨማሪም ጥቅም ላይ ሊውል የሚችል አይረን አለው፡፡

የቆዳ ውበትን ይጨምራል

ኮክ በውስጡ የያዛቸው ሚኒራሎችና ቫይታሚኖች ቆዳችንን ጤናማ ከማድረጋቸውም በላይ ቀለሙን እና ማራኪነቱን እንደጠቀ እንዲዘልቅ ያደርጋሉ፡፡

ነውጠኛ ህፃናትን ያረጋጋል

የኮክ ተክል አበባው ከስኳርና ከማር ጋር ተፈልቶ እንዲጠጡ ሲደረግ እረፍት የለሽ ህፃናት እንዲረጋጉ የማድረግ አቅም አለው፡፡ 80 በመቶ የኮክ ክፍል በውሃ የተሸፈነ ሲሆን ጥሩ የፋይበር መገኛም ነው፡፡ ክብደታቸውን ለመቀነስ የሚፈልጉ ሰዎች አዘውትረው ኮክብ ቢመገቡ ይጠቀማሉ፡፡

የጥገኛ ተዋህሲያን ፀር

ኮክ በአንጀት ግድግዳ ተለጥፈው የሚኖሩ ፓራሳይቶችንና ትላትሎችን ጠራርጎ በማስወገዱ ይታወቃል፡፡ በፓራሳይቶችና ትላትሎች የተነሳ ለሚከሰቱ የጤና ችግሮችም መፍትሄ ሰጪ ነው፡፡

የሆድን ጤንን ይጠብቃል

ኮክን በቋሚነት መመገብ የሆድን ጤንነት ይጠብቃል፣ ድርቀትንም ያስወግዳል፡፡ ጥናቶች እንደሚያሳዩት ከሆነ ከኮክ የምናገኛቸው አንቲ አክሲዳንቶች (በሽታ ተከላካዮች) የትኛውም አይነት የካንሰር ዝርያ በሰውነታችን ውስጥ እባጭ እንዳይፈጥር ይከላከላሉ፡፡

ለበርካታ ህመሞች ፈውስ ነው

ኮክን በቋሚነት በመመገብ ብቻ ልንከላከላቸው ወይንም ልንፈውሳቸው የምንችላቸው በበርካታ ለህይወት አስጊ እንዲሁም ሌሎች ህመሞችና በሽታዎች አሉ፡፡ ከነዚህም ውስጥ በደም ውስጥ እና ሰውነታችን ቲሹዎች ውስጥ የአልካሊኒቲ መጠን ሲቀንስ የሚከሰተው acidosis የደም ማነስ፣ አስም፣ የፊኛ እና የኩላሊት ጠጠሮች፣ ሮንካይትስ፣ ሆድ ድርቀት፣ ደረቅ ሳል፣ የጨጓራ ህመም፣ ከፍተኛ የደም ግፊት፣ ደካማ የምግብ መዋሀድ ስርዓት እና ለሌሎችም ህመሞችና በሽታዎች ፈውስና ተከላካይ ነው፡፡

በእያንዳንዱ 100 ግራም ኮክ ውስጥ የምናገኘው የካሎሪ መጠን 46 ብቻ በመሆኑ ክብደታቸውን ለመቀነስ የሚያስቡ ሰዎች በቋሚነት ቢወስዱት ክብደታቸው እንዲጨምር አያደርግም፡፡

ኮክ ትላትሎችን ከአንጀት አካባቢ ማስወገዱ ብቻ ሳይሆን እነዚህ ፓራሳይቶች ተደጋጋሚ ጥቃት እንዳይደርስብንና በሚያስከትሉት ጉዳት የተነሳ ለሌሎች በሽታዎች እንዳንጋለጥ ከፍተኛ ጠቀሜታ ይሰጣል፡፡

ኮክ በተፈጥሮው ቶሎ ቶሎ የሚያሸና (diuretic) በመሆኑ የኩላሊትን ስራ ያቃልላል፣ ሽንት ቶሎ ቶሎ እንዲወገድ በማድረግ ፈሳሽ እንዳይቋጠር ያደርጋል፤ ይህም የመገጣጠሚያ አካላት ላይ የሚደርሰውን ህመምና ስቃይ ይቀንሳል፡፡ ኮክ Carotenoids በተሰኘው የቫይታሚን ኤ አይነት የበለፀገ ነው፡፡ ይህም ጎጂ የፀሐይ ጨረሮች በአይኖቻችን ላይ ጉዳት እንዳያደርሱ ይከላከልልናል፡፡

ማሳሰቢያ፡-

የኮክ ፍሬ ለሰው ልጅ ጤና ጎጂ የሆኑትን Cryogenic glycosides የተባሉ ንጥረ ነገሮችን ይዟል፡፡ እነዚህ ንጥረ ነገሮች ሲሰባበሩ ወደ hydrogen cyanide gases ይቀየራሉ፡፡

ይህ ዘገባ በዘ-ሐበሻ ጋዜጣ ቁጥር 63 ታትሞ ወጥቷል።

ለፈለጉት የጤና ዘገባ Tenaadam.com

 


ሰኔ 15 የሰማታት ቀን ነው!

$
0
0

Abrha Destaሰኔ 15 የሰማእታት ቀን ነው። ሰኔ 15, 1980 ዓም በሐውዜን ከ2500 በላይ ንፁሃን ዜጎች በአንድ ፀሓይ የተጨፈጨፉበት ቀን ነው። ጭፍጨፋው የህወሓት እጅ እንደነበረበት ይነገራል። ይህ ማለት ቦምቡ የጣሉት ጀቶች የህወሓት ነበሩ ማለት አይደለም። ህወሓት በግዜው በሓውዜን ከተማ ጉባኤ እንደሚያደርግ ሆን ብሎ (የህዝብ ድጋፍ ለማግኘት) ለደርግ የሐሰት መረጃ አስተላልፏል። ብዙዎቹ የደርግ ጀነራሎችና መርማሪዎች የህወሓት “ስርዒት” ነበሩ። የአብዛኞቹ የደርግ ባለልስጣናት ፀሓፊዎች የህወሓት ስርዒት (ሰላዮች) ነበሩ። (አግአዚ ኦፕሬሽን ፊልም ይመልከቱ)። ለህወሓት የሚሰሩ ወታደራዊ መኮነኖችና ፓይለቶች ነበሩ።

የሐውዜን ደብዳብ የታቀደ ድራማ ስለመሆኑ ጥርጥር የለውም። ነገር ግን ደርግም ሐላፊነት ይወስዳል። ደርግ መንግስት እስከነበረ ድረስ ህዝብን ማዳን ነበረበት፤ መረጃው ማስተካከል ነበረበት። ሲጨፈጨፍ የነበረው ሰለማዊ ሰው እንጂ ታጣቂዎች እንዳልሆኑ ይታወቅ ነበር። ስለዚህ ሁለቱም ሐላፊነት ይወስዳሉ።

ህወሓት መጥፎ ተግባሩ እንዳይታወቅ በመስጋት ድራማውን የሚያውቁ ታጋዮች እንዲረሸኑ ተደርጓል። ከድር የተባለ ታጋይ “ምን ስንል ነበር? አሁን ምን እያደረግን ነው?” ብሎ በመጠየቁ ተገድሏል። ዳዊት የተባለም “በሐውዜን የተደረገው ነገር ስህተት ነበር” ብሎ በመከራከሩ ምክንያት ተረሽኗል። ከዛ ጦፍ ተልኳል ተብሏል።

አሁንም ይሄ ጉዳይ አለ። በሐውዜን ጉዳይ ጥናት ያደረገ የሐውዜን ተወላጅ የሆነ ጋዜጠኛ አፈወርቂ አርአያ የሐውዜን ጉድ በማጋለጡ ምክንያት ታስሮ ነበር፤ አሁን ደብዙ ጠፍቷል። ሚስጥር ያጋልጣል በሚል ስጋት እንዲጠፋ ተደርጓል (የት እንዳለ የምታውቁ ንገሩኝ)። ሌላ ገብረአነንያ ገብረስላሴ የተባለ የሐውዜን ተወላጅ “ሓመድ ሓውዜን፡ መን ንመን?” በሚል ርእስ ብዙ ሚስጢሮች በማጋለጡ ምክንያት በሰበብ አስባቡ በመቐለ ከተማ ዓዲሓቂ ፖሊስ ጣብያ ያለ ምንም ፍርድ ለሦስት ወራት ታስረዋል፤ አሁንም እዛው በእስር ይገኛል።

ህወሓት ከደሙ ንፁህ ከሆነ ስለጉዳዩ የሚናገሩ ሰዎችን ማሳሰርና እንዲጠፋ ማድረግ ለምን ፈለገ? የሐውዜን ጉዳይ አልፏል። ማስታወስ አንፈልግም፤ ይሰማናልና። ለፖለቲካ ፍጆታ መዋልም የለበትም። ግን የእስርና እንግልት ምንጭ ደግሞ መሆን የለበትም። ከጉዳዩ ጋር በተያያዘ ሰዎች መታሰር የለባቸውም።

የሆነ ሁኖ አልፏል። የኛ ያሁኑ ጉዳይ የሐውዜኑ ዓይነት ጨፍጫፍ በሰዎች ላይ እንዳይደገም መከላከል ነው። ዳግም ደም መፍሰስ የለበትም። ስለዚህ ህወሓትም ይፈፅመው ደርግ መደርጉ ስህተት ነው። ስሀተት በስህተትነቱ እናወግዘዋለን። ያሁኑ ጉዳይ ማነው የፈፀመው አይደለም። ያሁኑ ጉዳይ መፈፀም የለበትም፣ አልነበረበትም ነው።

ክብር ለሰማእታት! It is so!!!

የ2007 የመንግሰት በጀት ሚስጥር

$
0
0

(ግርማ ሰይፉ)

(ግርማ ሰይፉ)

ከግርማ ሰይፉ ማርይ
(የኢትዮጵያ ፓርላማ አባል)

የኢትዮጵያ በጀት በደንብ አድርጎ ለመረመረው ሀገሪቱ ያለችበትን ፖለቲካ ሁኔታ የሚያሳይ ነው፡፡ ይህም ማለት በበጀቱ ውስጥ የቻይና፣ ምዕራባዊያን ሀገሮች እንዲሁም የምዕራብ ሀገሮች ይዞታ የሚባሉት አለም አቀፍ ባንኮች እጅ በግልፅ የሚታይ ነው፡፡ እንደምታውቁት መንግሰት ለ2007 ዓመተ ምህረት ያቀረበው በጀት ብር 178.6 ቢሊዮን ነው፡፡ ዘጠኝ ቢሊዮን የአሜሪካ ዶላር አካባቢ ማለት ነው፡፡ መደበኛው ወጪ እና የክልሎች ድጋፍ ሙሉ በሙሉ በሀገር ውስጥ የሚሸፈን ሲሆን ዋና ዋና የካፒታል በጀት ደግሞ ከመደበኛ ወጪ እና ክልሎች ድጋፍ ከሚተርፈው አነሰተኛ የሀገር ውስጥ ገቢ እና ለበጀት ጉድለት ለመሸፈን ከታሰበው ከሀገር ውስጥ ባንኮች ብድር ይሸፈናል ተብሎ የሚጠበቅ ነው፡፡ ከአጠቃላይ በጀቱ 19.2 በመቶ ከእርዳታና ብድር ይሸፈናል በዝርዝር ሲታይ ግን የመደበኛ በጀቱ 21.8 ከመቶ፣ የካፒታል በጀቱ ደግሞ 36.5 ከመቶ የሚሸፈነው ከብድርና እርዳታ ነው፡፡
ስንት ሰው እንደሚያስታውስ ባላውቅም የቀድሞ አዲስ ጉዳይ ጋዜጣ (ሁሌም ጋዜጣ ሳስብ የሚናፍቀኝ) በአንድ ወቅት የቀረበን በጀት ይህ በጀት ኢትዮጵያዊ በጀት ነው ወይ? የሚል ጥያቄ አንሰቶ ነበር፡፡ የበጀትን ዜግነት የጠየቀበት ገፊ ምክንያት በዚያን ሰሞን መወያያ፤ በአሁኑ ጊዜ ጠርናፊ ህግ የሆነውን የሲቪል ማህበራት ህግ ነበር፡፡ ይህ አፋኝ ህግ ማነኛውም በኢትዮጵያ ውስጥ የሚንቀሳቀስ ሰቪል ማህበር በጀቱ ከአስር በመቶ በላይ ከውጭ ከሆነ ኢትዮጵያዊ አይደለም ነው የሚለው፡፡ አሁን በሀገራችን የሚንቀሳቀሱት ብዙዎች መንግሰታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች የተመዘገቡት በኢትዮጵያዊነት ሳይሆን “ረዚደንት” በሚል ቅፅል ነው፡፡ አዲስ ጉዳይ ጋዜጣ ይህን በጠየቀበት ወቅት የሀገሪቱ በጀት ከ40 በመቶ በላይ ከውጭ እርዳታ ሰለነበር ይህ መንግሰት ይህን ያህል ከውጭ የሚያገኝ ከሆነ ኢትዮጵያዊ አይደለም የሚል መከራከሪያ ይዞ ወጥቶ ነበር፡፡ ይህን ሰፋ አድርገው በመተርጎም አንድ አንድ ሰዎች የገቢ ምንጭ ዜግነት የሚወስን ከሆነ ብዙ ኢትዮጵያዊያን ከውጭ ከሚኖሩ ዘመዶቻቸው በሚላክላቸው ገንዘብ የሚተዳደሩ ስለሆነ ዜግነታቸው ኢትዮጵያዊ መሆን የለበትም ብለው ነበር፡፡ ስላቅ መሆኑ ነው፡፡ ያለበለዚያ ደግሞ የሚልኩላቸው ዘመዶቻቸው ዜግነት ያልቀየሩ በመኖሪያ ፍቃድ (ረዚደንት) የሚኖሩ መሆናቸውን ማረጋገጥ ይጠበቅባቸዋል፡፡
ethiopia-parliament
የሰዎችን ወይም የድርጅቶችን ዜግነት ኢትዮጵያዊ ወይም የውጭ ለማድረግ የገቢ ምንጭ መስፈርት መሆን የለበትም የሚለውን መከራከሪያ መንግሰት በዋዛ ያለፈው እንዳይመስላችሁ፡፡ መፍትሔ ብሎ የያዘው በተቻለ መጠን መንግሰት በጀቱን በመከፋፈል እና የተወሰኑት ወደ ጎን በማድረግ የብድርና የእርዳታ ገንዘቡ እንዳይታይ ማድረግ ነው፡፡ ለዚህም ነው መንግሰት ከፍተኛ መዋለ ንዋይ ከሚፈስባቸው የመሰረተ ልማቶች ውስጥ ዋና ዋና የሆኑትን ለምሳሌ እነ ቴሌ፣ መብራት ሀይል፣ ባቡር፣ የመሳሰሉት በሪፖርት ውሰጥ በስፋት እንደሰኬት ተካተው በበጀት ውስጥ ግን አይታዩም፡፡ ሉሎች ፋብሪካዎች ለምሳሌ ስኳር ፋብሪካ፣ ማዳበሪያ ፋብሪካ የመሳሰሉት ትልልቅ የመንግሰት ፕሮጀክቶቸ በበጀት ውስጥ የሉም፡፡ እነዚህ ከፍተኛ መዋለ ንዋይ የፈሰሰላቸው የመንግሰት ኢንቨስትመንቶች ከበጀት ውሰጥ እንዲወጡ የተደረጉት ደግሞ ብዙዎች በብድር የሚሰሩ ናቸው፡፡ የእነዚህ ፕሮጀክቶች የብድር ሂሣብ በበጀት ውስጥ ቢደመር የመንግሰትን በጀት ዜግነቱ ኢትዮጵያዊ ላይሆን ነው ማለት ነው፡፡ ለነገሩ በሲቪል ማህበራት ትርጉም እነዚህ ሁሉ ተቀንሰው አሁን የቀረበው የመነግሰት በጀት ኢትዮጵያዊ በሚያደርገው ደረጃ ላይ አይለም፡፡ ምክንያቱም ከአጠቃላይ በጀቱ 19.2 በመቶ ከውጭ ብድርና እርዳታ የሚገኝ ስለሆነ ማለት ነው፡፡

መንግስት በበጀት ውስጥ ያካተታቸው በእርዳታና ብድር የተገኙ አብዘኞቹ የካፒታል ወጪዎች ለኤኮኖሚ ሴክተር መንገድ፣ ግብርና እና ውሃ ሲሆን፤ እርዳታው ደግሞ ለጤናው ሴክተር የተመደበ ነው፡፡ የእነዚህ ገንዘቦች ዋናኛ ምንጮች ደግሞ የኒዎ ሊብራል አራማጆች የሚባሉት መንግሰታት እና የእነዚሁ መንግሰታት ይዞታ ናቸው የሚባሉት ባንኮች የሰጧቸው ብድሮች ናቸው፡፡ እነዚህ መንግሰታት እና በቁጥጥራቸው ስር ያሉት የፋይናንስ ተቋማት ኢትዮጵያዊያን ጤናቸው እንዲጠበቅ የተሻለ መንገድ እንዲኖረን፣ ምርታማ ግብርና እንዲሁም ንፁህ ውሃ እንዲኖረን ዕርዳታና ብድር እየሰጡን፤ በሌላ በኩል ደግሞ ብጥብጥ እንዲነሳ የቀለም አብዮት ይደግፋሉ ብሎ ስጋት ውስጥ መውደቅ አይቃረንም ወይ? ይህ በእውነት የአብዮታዊ ዲሚክራሲ ወይም የልማታዊ መንግሰት ቅዠት ይመስለኛል፡፡
በጣም የሚያስገርመው ደግሞ በዋነኝነት ከፍተኛ እርዳታ የሚሰጡን መንግሰታዊ ባልሆኑ ድርጅቶች በኩል አድርገው በቀለም አብዮት ሊያጠፉን ነው የሚባሉት የኒዎ ሊብራል አራማጅ ተብለው የተፈረጁት ሀገሮች መንግሰታት ናቸው፡፡ ከነዚህ ውሰጥ ቻይና እንደ መንግስት የምትሰጠን እርዳታ በሀገር ውስጥ ከውጭ ሀገር ዜጎች ምዝገባና የስራ ፈቃደ ከምናገኛው ያንሳል፡፡ ከሌሎቹ ሀገራት ጋር ሲነፃፀር ደግሞ ከአንድ መቶኛ ያነሰ ነው፡፡ ቻይና ሀገራችን በበጀት ውስጥ ከተካተተው ብድር ከ59 በመቶ በላይ ሰጥታናለች፡፡ ይህ ቻይና የሰጠችን ብድር ብዙ ስለሆነ ሳይሆን መንግሰታት ለኢትዮጵያ የሰጡት ብድር እጅግ ዝቅተኛ ከመሆኑ የመጣ ከፍተኛ የመቶኛ ድርሻ ነው፡፡ ቻይና በጀት ውስጥ ባልገባው ብድር ከፍተኛ አበዳሪያችን ነች፡፡ የቻይና ብድር በዋነኝነት በበጀት ውስጥ ባለተካተቱት ከፍተኛ የመንግሰት የመሰረተ ልማቶች እና የኤኮኖሚ ሴክተሮች ላይ ነው፡፡ ለምሳሌ ከበጀት እንዲወጣ የተደረገውን የቴሌን ማስፋፊያ ብቻ ብንወሰድ ወደ 32 ቢሊዮን ብር ወይም 1.6 ቢሊዮን በላይ የአሜሪካን ዶላር በ2007 በጀት ተብሎ የተያዘውን 18 ከመቶ ይሆናል፡፡ ይህ ገንዘብ በጀት ውስጥ ቢታይ እና የመንግሰትን የዜግነት መስፈርት ብንጠቀም መንግሰት ኢትዮጵያዊ ነው ለማለት ይቻላል ወይ? በጀት የመንግሰትን አቅም የሚያሳይ መለኪያ ነው በሚለው ልማዳዊ መለኪያ ለመጠቀም ለሚፈልግ ለቀጣይ ዓመት የቀረበው በጀት ትክክለኛውን የመንግስት ጡንቻ የሚያሳይ ነው ብለን ለመውሰድ እንቸገራለን፡፡

የኢኮኖሚና ፋይናንስ ሚኒሰትሩ አቶ ሶፊያ አህመድ በዚህ ጉዳይ በተደጋጋሚ በግንባር ቀደምነት የሚያነሱት የኢትዮጵያ አየር መንገድን ነው፡፡ የኢትዮጵያ አየር መንገድ በዕዝ ኢኮኖሚ በሚባለው በደርግም ጊዜ ቢሆን ሪፖርቱን በይፋ ያቀርባል አቶ ሶፊያ ግን ይህን እንዲያደርግ ያለበትን ዓለማ አቀፋዊ ጫና የምንረዳ አይመስላቸውም፡፡ ያለበለዚያ ቦይንግ መግዣ ገንዘብ ሊገኝ እንደማይችል ግልፅ ነው፡፡ አሁን እኛ የግልፅነት ችግር አለባቸው እያልን ያለነው የብረታ ብረትና ኢንጂነሪን የሚባለው አስማተኛ ድርጅት የሚሰራው ሰራ የሚያገኘው ገቢና ወጪው በግልፅ አይታወቅም ነው፡፡ እጅግ ብዙ ሀብት ፈሶበትም የሚያመጣው ትርፍ ተመጣጣኝ አይደለም እያልን ነው፡፡ በቅርቡ ከመንግሰት ድርጅቶች ይገዛው የነበረውን የወዳደቁ ብረቶች ግዢ እንዲያቆም መታዘዙ ይታወቃል፡፡ ለምን? የፀረ ሙስና እና ሰነምግባር ኮሚሸን እነዚህ ተቋማት ለምዝበራ የተጋለጡ እንደሆነ ሪፖርት አቅርቧል፡፡ ለነገሩ ይህ ድርጅት ተጠሪነቱም ለመንግሰት የልማት ድርጅት አይደለም፡፡ ሌሎቹም ኮርፖሬሽኖች ለምሳሌ የሰኳር ኮርፖሬሽን ስር ነው የሚባለው ተንዳሆ የሰኳር ፕሮጀክት ያለበትን ጉድ የማያውቅ ያለ አይመስለኝም፡፡

በጀት ውስጥ የገባውን የመከላከያ በጀት ስንመለከት ደግሞ በየሳምንቱ እሁድ በሚያቀርበው የቴሌቪዥን ፕሮግራ በነፃ ገበያ ሰርዓት እየተወዳደረ መነገዱን ቢነግረንም፡፡ በግልፅና በሰውር የሚሰራቸው የገቢ ማስገኛ ገንዘቦች እንዳሉት እየታወቀ ከውስጥ ገቢ የሚባል አንድም የገቢ ርዕስ በጀቱ ላይ አይታይም፡፡ ስለዚህ የኢትዮጵያ የመከላከያ በጀት ይህ ብቻ ነው ብሎ ለመውሰድ አይቻልም፡፡ የመንግሰት ጡንቻ በመከላከያ በኩል ከዚህ እንደሚበልጥ ለማወቅ ደግሞ ልዩ እውቀት አይጠይቅም፡፡ ለዚህ ነው የመንግሰትን ትክክለኛ ቁመና የሚያሳይ በጀት አይደለም የምንለው፡፡

እነዚህ እርዳታ እየሰጡን ብድር የማይሰጡን መንግሰታት ምክንያታቸው ምንድነው? ብሎ መጠየቅም ተገቢ ይመሰለኛል፡፡ በኒዮ ሊብራል አሰተሳሰብ ተፈርጀው ሀገራችን ላይ የቀለም አብዮት ሊያመጡ ያሴራሉ የሚባሉት ሀገራት በዋና ዋና የንግድ እና ኢንቨስትምነት ውስጥ እጃቸውን ለማስገባት ወደኋላ ያሉት ለምንድነው? በተቃራኒው ደግሞ ቻይና በእነዚህ ወሳኝ የኤኮኖሚና የንግድ ኢንቨስትመንት ውስጥ እጇን በሰፊው የምትዘረጋው ለምንድነው? ብሎ መጠየቅ እና መልስ መሻት ግድ ይላል፡፡

በእኔ እምነት የምዕራባዊያን መንግሰታት በኢትዮጵያ ውስጥ ባሉ የኢኮኖሚ መስኮች ውስጥ ለመሳተፍ ውሳኔ የሚሰጡት መንግሰታት ሳይሆኑ በየሀገሮቻቸው ያሉት የግል ባለሀብቶች ናቸው፡፡ የመንግሰታት ድርሻ ለባለሀብቶች ትክክለኛ መረጃ እንዲደርሳቸው ማድረግ እና ተገቢውን ከለላ መስጠት ነው፡፡ የግል ባለሀብቶች ደግሞ መረጃ የሚያገኙት ከኢቲቪ አይደለም፡፡ በተለያየ መልኩ በሀገራችን ያለውን ሁኔታ አብጠርጥረው ያውቁታል፡፡ እንደ ምሳሌ በቅርቡ በኦሮሚያ ክልል በሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች የተከሰተው ዓይነት ብሔርን መሰረት ያደረገ ብጥብጥ ከፍተኛ ትርጉም አለው፡፡ አንድ አንዶች እንደሚያስቡት በአዲስ አበባ እና በዙሪያዋ ያሉ ከተሞች የተቀናጀ ማሰትር ፕላን ዝግጅት ነው ብለው አይወስዱትም፡፡ የዓለም አቀፍ የሰብዓዊ መብት ተከራካሪዎችና የሰጋት ደረጃ የሚተነትኑ ድርጅቶች የሚያወጧቸው ሪፖርቶች ትርጉማቸው ከፍ ያለ ነው፡፡ በሀገሪቱ ውሰጥ ያለው የዲሞክራሲያዊ ሰርዓት በተለይም በየምርጫ ወቀት የሚፈጠሩ ሰጋቶች፤ መንግሰት የሚያወጣቸው አዋጆች፣ ደንቦች እና መመሪያዎች ተገማችነት፤ በአጠቃላይ ለኢንቨስትመንት ያለው ምቹ ሁኔታ ወሳኝ ግብዓቶች ናቸው፡፡ ዝም ብሎ በኢቲቪ የሚለፈፍ የገፅታ ግንባታ ፕሮፓጋንዳ ተጠቅመው የኢንቨስትምነት ውሳኔ አይሰጡም፡፡
በተቃራኒው የቻይና መንግሰት በከፍተኛ ደረጃ አፍሪካን ለመቆጣጠር ባለው ፍላጎት መነሻ እንዲሁም ውሳኔ የሚሰጡት የግል ባለሀብቶች ሳይሆን የቻይና መንግሰት በመሆኑ ውሳኔዎች በአብዛኛው ኤኮኖሚያዊ አዋጭነት ብቻ ሳይሆኑ የፖለቲካ ጭምር ናቸው፡፡ በአሁኑ ጊዜ ቻይና በዓለም ላይ ከፍተኛ ብድር ሰጪ ሀገር ነች፡፡ ለአማሪካ ጭምር፡፡ በቻይና የግል ሴክተሮች በዓለም አቀፍ ደረጃ ኢንቨስት ለማድረግ ገና አልደረሱም፡፡ ቻይና እንደ ሀገር ያላትን ከፍተኛ ቁጠባ በዓለም ላይ ኢንቨስት ለማድረግ እየተጠቀመችበት ነው፡፡ ቻይና በሙሉ በሚባል ደረጃ የምትሰጠንን ብድር የሚጠቀሙበት የቻይና ኩባንያዎች ናቸው፡፡ እነዚህ ኩባንያዎች ያለውን ስጋት በሚያካክስ ደረጃ ትርፋቸውን በአጭር ጊዜ ለማግኘት ይገባሉ በአሁኑ ሰዓት ቴሌን የወሰዱት ሁለት የቻይና የመንግስ ኩባንያዎች ናቸው፡፡ በተለያየ ስም የሚሰሩ፡፡ ቻይና የምታስገርመው እነዚህ የመንግሰት ኩባንያዎች ጉቦ የመሰጠት ጭምር አቅም አላቸው፡፡
እንደ ማጠቃለያ ለኢትዮጵያ የተበጀተው በጀት ብር 178.6 ቢሊዮን በጀት እንደ ሀገር ሲታይ አጅግ ዝቅተኛ ነው፡፡ ኢትዮጵያ 90 ሚሊዮን ህዝብ የሚኖርባት ከመሆኗ አንፃር እና በቅርቡ ደግሞ ዓመታዊ የነብስ ወከፍ ገቢያችን ብር 11 ሺ (550 የአሜሪካ ዶላር) ደርሶዋል ከተባልን ይህ በጀት ከእያንዳንዱ ሰው በወር የገቢውን 1.5 ከመቶ መዋጮ ሊሸፍነው የሚችለው ነው፡፡
ቸር ይግጠመን

ማስታወቂያ –ሰላማዊ ትግል 101 መጽሐፍ በግርማ ሞገስ

$
0
0

Girmas' book 2

ሰላማዊ ትግል 101 የተባለው በአይነቱ የመጀመሪያ የሆነው አዲስ መጽሐፍ በአዲስ አበባ እና በሌሎች የኢትዮጵያ ከተሞች ገበያ ላይ ውሏል። ሰላማዊትግል 101 የተዘጋጀውበሰላማዊትግልየኢትዮጵያን ህዝብ የመንግስት እና የአገሩ ባለቤት በማድረግ ኢትዮጵያን ወደ ዴሞክራሲለማሸጋገር የሚሹአገርወዳድኢትዮጵያውያንበተለይም ወጣቱ ኢትዮጵያዊ የሆነ ትምህርታዊየመወያያመጽሐፍእንዲኖረውታቅዶ ነው።ስለዚህ ሰላማዊ ትግል 101 በአቀራረቡም ሆነ በይዘቱ የውጭ አገር ቅጅ ሳይሆን ኢትዮጵያዊ ነው።

ለዘመናት በእርስ በርስ ጦርነት (Civil War) ሲፈጸም የነበረው የመንግስትሽግግርባህላችንንየግድ ማቆም እንዳለብን ግንዛቤ ለመስጠት ሰላማዊትግል 101 ከአክሱም ዘመን አንስቶ እስከ ዛሬ ድረስ የተደረጉት የመንግስት ሽግግሮች በህዝባችን እና በአገራችን ላይ ያደረሱትን አሳዛኝ ሃቅ በጭሩ ይተርካል።

ከአልበርትአነስታይንሰላማዊትግልምርምር ተቋምዘመናዊስራዎችውስጥ ጠቃሚዎቹን አቅልሎ ከማቅረቡ በተጨማሪ መጽሐፉ በ232 ገጾቹ ኢትዮጵያ ለምን ኋላ እንደቀረች፣ ሰላማዊ ትግል ከክርስቶስ ልደት ቀደም ብሎ ጀምሮ በኢትዮጵያ እና ከኢትዮጵያ ውጭ ያደረገውን እድገት፣ የመንግስት ስልጣን ባለቤት ህዝብ ነው የሚለው ጽንሰ አሳብ ከፖለቲካ ኃይል ምንጮች ባለቤትነቱ ጋር ያለውን ዝምድና፣ ፣ የፖለቲካ ኃይል ምንጮች እና የፖለቲካ ድጋፍ ምሶሶዎች ምን እንደሆኑ፣ ከ200 የሰላማዊ ትግል መፈጸሚያ መሳሪያዎች ውስጥ ዋናዎቹን፣ ሰላማዊ ትግል ህዝብን እንዴት የራሱ ነፃ አውጭ እንደሚያደርገው፣ በሰላማዊ ትግል የሲቪክ ድርጅቶች ሚና ምን እንደሆነ፣ ሴቶች ከሰላማዊ ትግል ጋር ያላቸው ተፈጥሮዋዊ ትስስር፣ በአሜሪካ አፍሪካ-አሜሪካውያን ለነፃነት ያደረጉት ሰላማዊ ትግል በሙሉ በቀላሉ ይተነትናል።

ሰላማዊ ትግል 101 በምርጫ እና በሰላማዊ ትግል መካከል ያለውን ትግግዝ ያብራራል። በተጨማሪ ዴሞክራሲ በዳበረበት በምዕራቡ አለም እና አምባገነኖች በሚገዟቸው አገሮች የሚደረጉ ምርጫዎች የተለያዩ መሆናቸውን፣ በአምባገነን አገሮች በሚደረጉ ምርጫዎች በሰላማዊ ትግል የህዝብ ድምጽ እንዳይሰረቅ ማድረግ እንደሚያስፈልግ ግንዛቤ ለማስጨበጥ በሰርቢያና በዝምባቡዌ የተደረጉትን ምርጫዎች እና የተፈጸሙትን ሰላማዊ ትግሎች በንጽጽር ይተነትናል። የግብጽ ወጣቶች ስላደረጉት ሰላማዊ ትግል እና የምርጫ ፓርቲዎች ስለሰሩት ስህተት ቀርቧል።

የምርጫ ታሪካችንን በሚመለከት ደግሞ መጽሐፉ ከኃይለስላሴዘመነመንግስትጀምሮለ80 አመታትያህልበኢትዮጵያየተደረጉትንምርጫዎች ይገመግማል።  ግምገማው ለምርጫ 97 ትኩረት ይሰጣል። ምርጫ 2007ን አስመልክቶም መጽሐፉ በክልሎች እና በፌዴራል ደረጃ በሚደረጉ ምርጫዎች የምርጫ ፓርቲዎች ማድረግ ስለሚገባቸው ዝግጅቶችም ውይይት ይከፍታል። መልካም ንባብ። መልካም ውይይት።

 

 

 

 

 

 

 

 

 

በሐዋሳ በ3 ጣቢያዎች የታሰሩት የአንድነት ፓርቲ አባላት ዛሬም ፍርድ ቤት አልቀረቡም

$
0
0

(ፖሊስ ትናንት የአንድነትን ሰልፍ እንዲበተን ያደረገው እንዲህ ከተማዋን በመውረር ነበር)

(ፖሊስ ትናንት የአንድነትን ሰልፍ እንዲበተን ያደረገው እንዲህ ከተማዋን በመውረር ነበር)

ከሐሙስ ሰኔ 12 ጀምሮ እስከ ቅዳሜ ሰኔ 14 ማታ ድረስ በከተማው በሚገኙ የተለያዩ ጣቢያዎች ከ37 በላይ የፓርቲው አባላት እስካሁን ፍርድ ቤት አለመቅረባቸው የፍኖተ ነፃነት የፖሊስ ምንጮች ገለጹ፡፡ እንደ ፍኖተ ነፃነት ምንጮች ከታሰሩት አባላት መካከል አቶ በየነ መረባ የተባሉ የሐዋሳ የአንድነት ፓርቲ ፀሐፊ አንተን ፍ/ቤት አናቀርብህም ከጓደኞችህ ጋር ነው የምንቀላቅልህ በማለት ሲያስፈራሩዋቸው፣ የትኞችን ጓደኞቼን ብለው ሲጠይቁ እሱን ታየዋለህ በሚል ምላሽ እንደሰጧቸው ገልጸዋል፡፡ የሰመጉ የአዋሳ ተጠሪዎች ታሳሪዎቹ ፍርድ ቤት እንዲያቀርቧቸው ቢጠይቁም አይቀርቡም የሚል ምላሽ እንደተሰጣቸው ምንጮቻችን ጠቁመዋል፡፡

ምንጭ፡ ፍኖተ ነፃነት ጋዜጣ

Hiber Radio: ኦብነግ በአፋርና በሶማሌ ተወላጆች መካከል የተፈጠረው ውጥረት እንዳሳሰበው ገለጸ * የእንግሊዝ አዲስ ሕግ ጫት ያዘዋወረ 14 ዓመት ይቀጣል አለ

$
0
0

ጋዜጠኛ ሃብታሙ አሰፋ

ጋዜጠኛ ሃብታሙ አሰፋ


የህብር ሬዲዮ ሰኔ 15 ቀን 2006 ፕሮግራም

<... ...> አቶ ዳንኤል ሺበሺ የአንድነት ም/የድርጅት ጉዳይ ሀላፊ በወቅታዊ ጉዳይ ላይ ለህብር ከሰጡት መግለጫ የተወሰደ (ሙሉውን ያዳምጡት)

>

አቶ ረዳ መሐሪ የአፍሪካ ኮሞኒቲ ሴንተር ማኔጂንግ ዳይሬክተር የዓለም የስደተኞች ቀንን ምክንያት በማድረግ ካደረግነው ቆይታ (ሙሉውን ያዳምጡ)

<... ...>

ጋዜጠኛ ደረጄ በጋሻው የቀድሞ የአስኳል ጋዜጣ ዋና አዘጋጅ በኡጋንዳ የዓለም የስደተኞች ቀንና የኢትዮጵያውያን ስደት አስመልክቶ ከሰጠን ማብራሪያ(ሙሉውን ቃለ መጠይቅ ያዳምጡ)

ዋልድባን እንታደግ ቡድን ዘንድሮም እየተንቀሳቀሰ ነው

ዜናዎቻችን

የተባበሩት መንግስታት በኢትዮጵያ የሚፈጸመውን የሰብዓዊ መብት ጥሰት ለማጣራት ልዩ የአጥኚ ቡድን እንዲልክ ተጠየቀ

በአዋሳ የአንድነትን ሰልፍ ለማደናቀፍ የጸጥታ ሰዎች ቅስቀሳ ያደረጉ 32 የፓርቲውን አባላትና አመራሮች በልዩ ልዩ ፖሊስ ጣቢያ አስረዋል

አንድነት ዛሬ በጫና ያላካሄደውን ሰልፍ አዋሳ ላይ ደግሞ ሊጠራ ነው

ኦብነግ በአፋርና በሶማሌ ተወላጆች መካከል የተፈጠረው ውጥረት እንዳሳሰበው ገለጸ

ለግጭቱ የአገዛዙ እጅ አለበት ብሏል

በመኢአድና በአንድነት አባላት ላይ ጥቃቱ ቀጥሏል

የመኢአድ አባል በካድሬዎች ተደብድበው ሞቱ

የእንግሊዝ መንግስት ከቀጣዩ ሳምንት ጀምሮ ጫትን ሕገወጥ አደረገ

በአዲሱ ሕግ ጫት ያዘዋወረ የ14 ዓመት እስር ይጠብቀዋል

ከኦሮሚያ ክልል በሺህ የሚቆጠሩ የአማርና ተናጋሪ ኢትዮጵያውያን በሀይል ከአካባቢው እንዲለቁ ተደርገዋል

ድብደባና ግድያ የተፈጸመባቸው አሉ

ሌሎችም ዜናዎች አሉ

ከአንድነት ፓርቲ የተሰጠ ጋዜጣዊ መግለጫ

$
0
0

በተለየ ሁኔታ በደቡብ ክልል እየታየ ያለው መንግስታዊ አፈናና ፀረ-ሕግ አቋም እንዲገታ ትግላችንን አጠናክረን እንቀጥላለን!!!

UDJ Headባለፉት 23 ዓመታት የኢትዮጵያ ሕዝብ ስርዓቱ አምጦ የወለዳቸው ሀገራዊ አፈና፣ ማዋከብ፣ የመኖር ዋስትናን መንፈግ፤ ዜጎችን ማሰደድና ማሰር የተለመዱ ድርጊቶ ሆነው ኖረዋል፡፡ አሁንም በዚህ አስከፊ የአፈና መንገድ ጉዞውን ቀጥሏል፡፡ የስርዓቱ መንግስታዊ አፈናና ፀረ-ሕዝብ አቋም በመላ ኢትዮጵያ የተዘረጋ ቢሆንም ፓርቲያችን በእንቅስቃሴዎቹ ውስጥ እንደታዘበው በደቡብ ክልል በተለየ ሁኔታ ተጠናክሮ ቀጥሏል፡፡ በተለይም ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ በክልሉ የሚገኙ የተለያዩ ሹማምንቶች ባደረባቸው የገዥነት መንፈስ ሰላማዊ እንቅስቃሴዎችን በማፈንና ብሎም ያለምንም ማስረጃና ምክንያት ሰላማዊ ታጋዮችን ወደ እስር ቤት በመክተት ተግባራዊ እያደረጉ ይገኛሉ፡፡

ከዚህ በፊት በክልሉ በወላይታ ዞን ሶዶ ከተማ የፓርቲያችን ከፍተኛ አመራሮች ከዞኑ አመራሮች ጋር ውይይት ሲያካሂዱ ድንገተኛ ወረራ ተደርጎና የግቢ በር ተሰብሮ ወደ እስር ቤት ተወስደው ነበር፤ ቁጫ ላይ ጠርተነው የነበረው ሰላማዊ ሰልፍም እንዲሁ በጉልበት፣ በእስርና አፈና እንዳይካሄድ ተደርጓል፤ ይባስ ብሎ ደግሞ የክልሉ ዋና ከተማ በሆነችው አዋሳ የጠራነው ሰላማዊ ሰልፍ ተገቢውን ህጋዊ ሂደት ቢያልፍም በህገ-ወጥ እስር እንዲጠናቀቅ ሆኗል፡፡ ይህ እውነትም በክልሉ በተለየ ሁኔታ መንግስታዊ አፈናና ፀረ-ሕግ አቋም እንዳለ ያረጋገጠ ነው፡፡

አዋሳ ከተማ ላይ የጠራነው የተቃውሞ ሰልፍ በሚካሄድበት ማግስት ከ30 በላይ አባሎቻችንን፣ የዞኑን አመራሮችና ከአዲስ አበባ ለቅስቀሳ የሄደውን ቡድን ከነ መኪናው ወደ እስር ቤት በመውሰድ መንግስታዊ አፈናውን በገሀድ አሳይተዋል፡፡ በደቡብ የተፈጠረው የገዥነት መጥፎ መንፈስ የተጠናወታቸው የታች ባለስልጣናት ህግ በአደባባይ እንደረገጡ ታይቶበታል፡፡ አሳሪዎቹ በቅስቀሳ ላይ የነበሩት አባላትና አመራሮቻችን ‹‹ህጉን ጠብቀን አሳወቅን፣ የእውቅናውን ደብዳቤ መስጠት ይህን ሊሰራ የተቀመጠው አካል ድርሻ ነው፡፡ እውቅና ወረቀቱን የሚሰጠው አካል ስራውን ስላልሰራ እኛ ስራ ማቆም የለብንም፡፡›› ለሚለው መልስ ስላልነበራቸው ማሰርን እንደ መፍትሔ ወስደዋል፡፡ ህገወጡን የአትቀስቅሱ ትእዛዝ ከመቀበል መታሰር እንደሚሻል እጃቸውን ለካቴና የሰጡ አባሎቻችንና አመራሮች አረጋግጠዋል፡፡

ፓርቲያችን እንደሚገነዘበው የህዝቡ የለውጥ ፍላጎት ገፍቶ በወጣ ቁጥር የአምባገነኖች መደናበር ያይላል፡፡ ሲደናበሩም ህግ ይጥሳሉ፣ ህዝብ ያሰቃያሉ፣ ሀገር ይበድላሉ፡፡ አፋኞች ያልተገነዘቡት እድሜ ልክ ዕየተጨቆኑ መኖር እንደማይቻል ብቻ ነው፡፡

አንድነት እንደዚህ አይነቱን አይን ያወጣ አፈናና ፀረ-ሕግ አካሄድ በቸልታ አይመለከተውም፡፡ በክልሉ ለመዝጋት እየተሞከረ ያለውን የህዝብ ጥያቄ ከህዝብ ጋር በመሆን መፍትሔ እንዲያገኝ እናደርጋለን፡፡ በህግም እንጠይቃለን፡፡ በክልሉ ነፃ ምርጫ እንዳይካሄድና ህዝቡ በንቃት እንዳይደራጅ እየተደረገ ያለ ጥረት አካልም ነው፡፡ ያለምንም ወንጀል የታሰሩ አባሎቻችንና አመራሮቹ ያለምንም ቅድመ ሁኔታ በአስቸኳ እንዲፈቱ የሚመለከተው አካል ሃላፊነቱን እንዲወጣ እያሳሰብን በደቡብ ክልል እየታየ ያለው መንግስታዊ አፈናና ፀረ-ሕዝብ አቋም መታገላችንን እንደምንቀጥል እናረጋግጣለን፡፡

                   ድል የህዝብ ነው!!!

                                            አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት)

                                                     ሰኔ 16 ቀን 2006 ዓ.ም

                                                           አዲስ አበባ

 

የአንድነት የአዋሳ ሰልፍ “በእስር ተጀምሮ በእስር ተጠናቀቀ”

$
0
0
(ፖሊስ ትናንት የአንድነትን ሰልፍ እንዲበተን ያደረገው እንዲህ ከተማዋን በመውረር ነበር)

(ፖሊስ ትናንት የአንድነትን ሰልፍ እንዲበተን ያደረገው እንዲህ ከተማዋን በመውረር ነበር)

ሰኔ ፲፬(አስራ አራት)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የሚሊዮኖች ድምጽ ለመሬት ባለቤትነት በሚል አንድነት ፓርቲ በአዋሳ ሊያካሂደው የነበረው ሰልፍ ፣ የሰልፉ አስተባባሪዎችና የፓርቲው የአመራር አባላት በመታሰራቸው ምክንያት ሳይካሄድ ቀረ።

ሰልፉ ከመካሄዱ አንድ ቀን ቀደም ብሎ በፓርቲው ቅስቀሳ የተደናገጡት የሚመስሉት የአዋሳ ባለስልጣኖችና ፖሊስ አባላት 37 የሚሆኑ በቅስቀሳ ላይ የተሰማሩ አመራሮችንና ደጋፊዎችን ይዘው በተለያዩ እስር ቤቶች አስረዋቸዋል።

በማግስቱ እስረኞችን ለመጠየቅና ስንቅ ለማቀበል ከሄዱት መካከልም አንዳንዶች መታሰራቸውን በስፍራው የሚገኘው የአንድነት ፓርቲ የአዲስ አበባ ህዝብ ግንኙነት ሃላፊ አቶ ያሬድ አማረ ለኢሳት ገልጸዋል።

ከአዲስ አበባ የሄዱና የአዋሳ የፓርቲው አመራሮች ፍርድ ቤት ሳይቀርቡና ክስ ሳይመሰረትባቸው በመታሰራቸው የረሀብ አድማ ያደረጉ ሲሆን፣ ዛሬ ሰኞ ፍርድ ቤት ይቀርባሉ ተብሎ እየተጠበቀ መሆኑን አቶ ያሬድ አክለው ተናግረዋል።

መድረክ በአዋሳ በከፍተኛ ወከባ ውስጥ ሆኖ የተቃውሞ ሰልፍ ማድረጉ ይታወቃል። አንድነት ፓርቲ በተለያዩ ክልሎች እየዞረ በርካታ ህዝብ የሚሳተፍበት ሰላማዊ ሰልፎችን እያደረገ ነው። በአዋሳው ሰላማዊ ሰልፍ በኦሮሞ ወጣቶች ላይ የተወሰደው እርምጃ፣ የኑሮ ውድነት፣ ከማንነት ጋር በተያያዙ የሚታዩት የሰብአዊ መብቶች ጥሰት እና የመሳሰሉት ጉዳዮች ይነሳሉ ተብሎ ይጠበቅ ነበር።

አንድነት በአዋሳ ለሚያካሂደው የተቃውሞ ሰልፍ ለክልሉ መንግስት የእውቅና ደብዳቤ ያስገባው ከአንድ ወር በፊት ነበር። የከተማው ምክር ቤት እስካለፈው አርብ ድረስ በጉዳዩ ላይ ውሳኔ ለመስጠት እየተነጋገርነበት ነው በማለት ሲያጓትተው ቆይቷል።

አንድነት ፓርቲ በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ “በተለየ ሁኔታ በደቡብ ክልል እየታየ ያለው መንግስታዊ አፈናና ጸረ ህግ አቋም እንዲገታ ትግላችንን አጠናክረን እንቀጥላለን” ብሎአል።

“የስርዓቱ መንግስታዊ አፈናና ፀረ-ሕዝብ አቋም በመላ ኢትዮጵያ የተዘረጋ ቢሆንም ፓርቲያችን በእንቅስቃሴዎቹ ውስጥ እንደታዘበው በደቡብ ክልል በተለየ ሁኔታ ተጠናክሮ ቀጥሏል” ያለው አንድነት፣ “በክልሉ የሚገኙ የተለያዩ ሹማምንቶች ባደረባቸው የገዥነት መንፈስ ሰላማዊ እንቅስቃሴዎችን በማፈንና ብሎም ያለምንም ማስረጃና ምክንያት ሰላማዊ ታጋዮችን ወደ እስር ቤት በመክተት ተግባራዊ እያደረጉት ” ነው ብሎአል።

በወላይታ ዞን ሶዶ ከተማ የፓርቲው ከፍተኛ አመራሮች ወደእስር ቤት መወሰዳቸውን፣ ቁጫ ላይ ተጠርቶ የነበረው ሰላማዊ ሰልፍም እንዲሁ በጉልበት፣ በእስርና አፈና እንዳይካሄድ መደረጉን የገለጸው አንድነት፤ የክልሉ ዋና ከተማ በሆነችው አዋሳ የተጠራው ሰልፍ በህገወጥ እስር መጠናቀቁን ገልጿል፡፡

“በክልሉ ለመዝጋት እየተሞከረ ያለውን የህዝብ ጥያቄ ከህዝብ ጋር በመሆን መፍትሔ እንዲያገኝ እናደርጋለን” የሚለው አንድነት ጉዳዩን ወደ ህግ እንደሚወስደውም ገልጿል።

ያለምንም ወንጀል የታሰሩ አባሎቻችንና አመራሮቹ ያለምንም ቅድመ ሁኔታ በአስቸኳ እንዲፈቱ የጠየቀው ፓርቲው ፣ በደቡብ ክልል እየታየ ያለውን መንግስታዊ አፈናና ፀረ-ሕዝብ አቋም እንደሚታገለው አስታውቋል።ዘግይቶ በደረሰን ዜና ደግሞ በቅስቀሳ ላይ የነበሩት አመራሮች የዋስትና መብታቸውን ተከልክለው ወደ እስር ቤት እንዲመለሱ ተደርጓል።

መስተዳድሩ ከጻፈው ደብዳቤ ለመረዳት እንደሚቻለው ሰዎቹ የታሰሩት በህገወጥ መንገድ ሲቀሰቅሱ ተገኝተዋል በሚል ነው።

Source: Ethsat


የ AESA ONE  ፕሬዚዳንት ራሳቸውን ከማህበሩ አገለሉ

$
0
0

 

ከ ኢትዮጵያውያን የስፖርት ፌዴሬሽን በሰሜን አሜሪካ ESFNA የተገነጠለው AESA ONE  ፕሪዚዳንት ራሳቸውን አገለሉ፤ግልፅነት  እና ተጠያቂነት ያለበት ኣሰራር እንዲሰፍን በመጠየቅ ባለፈው ማርች መልቀቂያ ያቀረቡት አቶ አክሊሉ ግደይ  በድርድር ከተመለሱ በሁዋላ ፣ ችግሩ በመቀጠሉ ግልፅነት የሌለውን አሰራር በመቃወም ከጁን 18/2014  ጀምሮ ራሳቸውን ማግለላቸውን ያሳወቁ ሲሆን፣ከእንግዲህ AESA ONE ጋ ር በተያየዘ ስማቸው እንዳይነሳ አሳስበዋል፤አቶ አክሊሉ ግደይ  ለAESA ONE  ቤተሰቦች በበተኑት የኢሜል መልዕክትት ተተኪ አመራር ተብለው ከተመረጡ 4 ሰዎች ርሳቸውን ጨምሮ ሶስቱ ድርጅቱን መልቀቃቸውንም አስረድተዋል፤የቀድሞዎቹ አመራሮች  አቶ ኣያያ   አረጋ እና አቶ ታምሩ አበበ ከማህበሩ ተወግደው ያላግባብ ተባረናል በሚል በክስ ላይ መሆናቸው ታውቐል፤ይህ እንዲህ እያለ በሚኒሶታው AESA ONE  ዝገጅት  ላይ ይዘፍናሉ ተበለው ፖስተራቸው ከተሰራጨባቸው ዘፋኞች ግርማ ተፈራ ያለፈቃዱ ፎቶገራፉ እንደወጣና እንደማይመጣ የቅርብ ምንጮች ገልጸዋል፤ሌሎቹ አርብ ጁን 27/2014  ይገባሉ፤

[ሙሉውንለማንበብእዚህይጫኑ]

 

4

From: “Aklilu>
Date: Jun 18, 2014 2:20 PM

Subject: Goodbye

To “Bisrat Meskel”

To my Aesaone family:

 

I wanted to say goodbye to all of you; I sent my resignation letter to our Chairman earlier today.  My goal in this organization had been to institutionalize transparency, accountability, honesty and professional discourse. I have fought all year to get these things in place.  However, as the underneath response to my latest request for transparency indicates I have failed to achieve my goal.  I will not detail all my concerns here; I have already shared them with the Chairman privately.  I hope he will make the necessary corrections.  For me however, this is the end of the road.  I do not want to be President nor do I want any part at all.

 

Some of you may wonder why I waited so long to disassociate myself if I had such strong concerns. The answer to that is the fact that I had already resigned in March but only returned because I was promised major changes promptly.  Unfortunately, the promised changes never came. I waited, waited and waited but now I can wait no more. Effective immediately I want any mention of my name to be taken off from Aesaone web-site, Facebook page or any other communication.

 

I wish you all Godspeed as I join the 2 other “new young leaders” that left before me into early retirement. That makes me the third of the original 4 “new leaders” to leave Aesaone in less than a year.

 

Sincerely,

 

Aklilu Gidey

2

በሀዋሳ ሰ.መ.ጉ እስረኞችን እንዳይጎበኝ ተከለከለ

$
0
0

ፍኖተ ነፃነት

በሃዋሳ ከተማ በእስር ላይ የሚገኙትን የአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ አባላትን ሁኔታ ለመመልከት ወደ ወደ ሃዋሳ እስር ቤቶች ያመሩት የሰብዓዊ መብት ጉባዔ ሀላፊዎች እስረኞቹን ለማግኘት እንደማይችሉና ከማንም ጋር እንዳይገናኙ ትዕዛዝ በመተላለፉ ምክንያት ታሳሪዎቹን ማግኘት እንዳልተቻለና የጣቢያ ሀላፊዎቹን ለማናገር የተደረገውም ጥረት እንዳልተሳካ አስረድተዋል፡

አንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ(አንድነት)ባሳለፍነው ሳምንት ሰኔ 15 ቀን 2006ዓ.ም በሃዋሳ ከተማ ሊያካሂድ የነበረውን ሰላማዊ ሰልፍ ተከትሎ በእስር ላይ የሚገኙት የአንድነት ፓርቲ አባላት ‹‹ፍትህን ተነፍገን ትግላችን አይቆምም ››በማለት ዛሬም ለ4ኛ ቀን በርሀብ አድማ ላይ ናቸው፡፡አባላቱ በቁጥጥር ስር ከዋሉበት ቅዳሜ እለት ጀምሮ በረሀብ አድማ ላይ ሲሆኑ በትላንትናው እለት ሰኞ ሰኔ 16 ቀን 2006 ዓ.ም በሀዋሳ ከተማ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ቀርበው በኢ/ፌ/ዲ/ሪ የወንጀል ህግ አንቀጽ 27(1-ሀ)32/1-ሀ/እና 257 ላይ የተመለከተውን በመተላለፍ በሚል የአዋሳ ከተማ ከፍተኛ ዐ/ሕግ ክስ ተመስርቶባቸው የዋስትና መብታቸው ተነፍጎ በእስር እንዲቆዩና ዓቃቤ ህግ ምስክሮቹን ለሰኔ 20 ቀን 2006 እንዲያሰማ ፍርድ ቤቱ ትዕዛዝ በማስተላለፉ ወደ እስር ቤት እንዲመለሱ ተደርጓል፡፡


10448208_657204214364516_9050720156707149922_n
10438349_657205647697706_637993046936063852_n

10450753_657204294364508_6267425299544943631_n

 

ሰበር ዜና ጅዳ ሳውዲ አረቢያ አንዲት ኢትየጵያዊት በጅዳ ቆንስል ግቢ ታንቃ ተገኘች ።

$
0
0

unnamed (1)በሳውዲ አረቢያ ጅዳ ቆንስላ ጽ/ቤት ግዜያዊ የስደተኞች መጠለያ ውስጥ እንዲት ኢትዮጵያዊት ታንቃ መገኘቷ የአካቢውን ማህበረሰብ ደረት ሲያስደቃ መዋሉን ቦታው ላይ የነበሩ የአይን እማኞች አረጋግጠዋል። ዛሬ በኢትዮጵያ ሰአት አቋ ጣጠር ከቀኑ 10 ሰአት ቆንስላው ጽ/ቤት ግቢ ውስጥ ታንቃ የተገኘቸው ወጣት በ 20 አመት የእድሜ ክልል ውስጥ የምትገኝ መሆኗን የሚናገሩ እማኞች በኮንተራት ለስራ መጥታ ከአሰሪዎቾ ባለመስማቷ በጅዳ የኢትዮጵያ ቆንስላ ግዜያዊ መጠለያ ኮንቴነር ውስጥ ለረዥም ወራት ስትሰቃይ የኖረች ሳትሆን እንደማትቀር ይናገራሉ ; ፡ በኢትዮጵያ ሰዓት አቋጣጠር ዛሬ ከቀኑ 10 አካባቢ እዚህ ቆንስላ ግቢ ውስጥ የታነቀቸውን ወጣት በአይናቸው ለማየት እድል ያገኙ እማኞች ወጣቷ እራሷን አንቃ ለመግደል ስትወራጭ አንገቷ ውስጥ የገባው ገመድ መስል ነገር ጉሮሮዋን ቆርጧ ወዲያው ሳይገድላት እንዳልቀረ ይገልጻሉ።

ይህ ዜና እስከ ተጠናከረበት ግዜ ድረስ የወጣቷ ሬሳ አለመንሳቱን የሚናገሩ ምንጮች በአካባቢው የፓስፖርተ እድሳት እና መስል ተዘማጅ ጉዳዩቹን ለማስፈጸም የቆንስላ ግቢውን አጨናነቀው እምባ ሲራጭ የነበሩ ኢትዮጵያውያን ከቆንስላው ጽ/ቤት እንዲወጡ መደረጋቸውን የአይን እማኞቹ አክለው ገልጸዋል ። ይህ በዚህ እንዳለ የሬሳ ጉዳይ የሚከታተለው እና የቀድሞ የኮሚኒቲ አመራር አቶ መሃመድ ሸህ ተፈቅዶለት ወደ ግቢው ሲገባ ያዩ ምንጮች ቦታው ላይ የሳውዲ ፖሊሶች እና ዲፕሎማቶች መገኘታቸውን አረጋግጠዋል ። የጅዳ ቆንስ ጽ/ቤት የእህቶቻችንን አስከሬን ሲያስተናገድ የመጀመሪያ ግዜው እንዳለሆነ የሚናገሩ ወገኖች በዲፕሎማቱ የአሰራር ድክመት በአንድ ወር ውስጥ ብቻ ለሁለተኛ ግዜ ታንቃ ህይወቷ ባለፈው ወጣት ተደናግጠው ሲጮጮሁ በነበሩ ኢትዮጵያውያን የቆንስላው ጽ/ቤት ድባብ ወደ መቃብር ስፍራ ነት ተለውጦ ማምሸቱን ይናገራሉ ።

በአሁኑ ግዜ በዚህ የቆንስላ ቅጥር ግቢውስጥ ከ 40 የሚበልጡ ተፈናቃይ የኮንተራት ሰራተኞች ከሰው እይታ ተገለው ይሚገኙ ሲሆን ባዶ ክፍሉ ውስጥ ያለምንም እርዳታ ሃገር ትገባላቹ በሚል ተስፋ መጋዘን ተቆልፎባቸው ለበለጠ ስቃይ እና መከራ እይተዳረጉ ከሚገኙ እህቶቻን መሃከል አብዛኛዎቹ የፈላ ውሃ በአሰሪዎቻቸው የተደፋባቸው የተድፈሩ እና ደሞዛቸው የተነጠቀ መሆኑ ይነገራል።፡፤ የወገኖቻችን ሞት ከሚፈበረከበት ሁለተኛው ማዕከል ጅዳ ከሆነው የ ቆንስላ ጽ/ቤት ግቢ ውስጥ በአንድ ወቅት አንድ የውሃ ጉድ ጓድ ውስጥ ሬሳዎ በተገኘ ኢትዮጵያዊት ጉዳይ የህ.ወ.ህ.ቱ አባል አቶ ገሬ ለወራት ወህኒ ቢወርዱም የሞቾ ምስኪን ጉዳይ ተድበስብሷ ሲቀር አቶ ገሬ ከወራት እስራት በኋላ በወጭ ጉዳይ ግፊት መፈታታቸው በህዝብ ዘንድ ተቃውሞ ማስነሳቱ አይዘነጋም።
Ethiopian Hagere ጅዳ በዋዲ

 

 

 

 

የሎሬት ህመሙ ቢያመኝ!

$
0
0

የሎሬት ህመሙ ቢያመኝ …
———–//———
ይሞላ ብዪ ስኳትን ፣
ህልሜ እልም እያለ ቢፈትነኝ
ለህሊናየ አድር ብዪ ስማስን ፣
ድካሙ ቢሸበርክኝ
ተስፋ አልቆርጥም ባልኩ በተጋሁ፣
ህመሙ ቢደቁሰኝ
ብላቴን ጌታ ታወሰኝ ፣
ጸጋየ ህመሙ ዘልቆ ወጋኝ
የጸጋየ ህመሙን ታመምኩ
መላ ቅጡን አስጠፋኝ ።
ውስጤ ቢደማ ቢታወክ ፣
የጸጋየ ሮሮ በአይነ ህሊናየ መጣብኝ
የመጨረሻው እስትንፋስ ቃሉ ፣
ሎሬት ህመሙ አመመኝ
“እኔ ለእኔ ኑሬ አላውቅም ” ብሎ ያለን
የስንብት ጸጸት ቃሉን አዘከረኝ ፣
……. …….. ……. ……… …….. ……
የጸጋየ ጸጸት …
“የማይሰማ ወጨት ጥጄ –
እፍ ስል የከሰመ ፍም፣
ውርዴም ይፈወሳል ብዬ -
የሰው እከክ ስዘመዝም፣
በሰው ቁስል መቁሰል በቀር –
እኔ ለኔ ኖሬ አላውቅም፡፡
የማይነጋ ህልም ሳልም –
የዘመን ደዌ ሳስታምም፣
የማያድግ ችግኝ ሳርም –
የማይድን በሽታ ሳክም፣
የሰው ህይወት ስከረክም –
እኔ ለኔ ኖሬ አላውቅም፡፡ ”
…… …….. ……. …….. …… ….. ……
ባይሰማ ባያየኝ አባት አለም ፣
ተስፋው በኖ የተለየንን
የቅኔው አባት መምህሩን ፣
10311727_10204297604786213_1298964279299971454_n
የጥበብ ሎሬት ፈላስፋውን
ድካም ልፋቱ መና ቀርቶ የታየውን ፣
“ግዴለም በተስፋ እንኑር አልኩት !” ጸጋየን
መላው ጠፍቶ ቢጨንቀኝ ፣
በተስፋ እኖር መስሎኝ ሳታልላት ደካማ ነፍሴን …
* ብላቴን ጌታ ጸጋየ ፣ ነፍስህን አራያ ገነት ያኑራት: (
በተጎዳ ስሜት … ይህችን ታክል ካልኩ ይብቃኝ! :(
ነቢዩ ሲራክ

ግልጽ ደብዳቤ!

$
0
0

ለሰባዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች!
ለጋዜጠኛ መብት ተከራካሪዎች!
ህሊና ላላቸው ወገኖች በሙሉ!
የዓለም ስደተኞች ቀን ጁን 20 በመላ ዓለም ይከበራል። በየዓመቱ አስደሳች መፈክሮች ይጻፋሉ።ይለጠፋሉ።ስብስባዎች
ይካሄዳሉ።ታላልቅ ሰዎች መልዕክት ያስተላልፋሉ።ስደት በዓለም ላይ እንደኑሮ ውድነት እየጨመረ ነው።ችግሩ የአፍሪቃ
መሆኑ ቀርቶ አውሮፓና ኤዢያንም እያዳረሰ ነው።እኔ እንኳን ከተሰደድኩባት Dec 9,2005 ወዲህ
ኬንያ፥ሊቢያ፥ቱንዚያ፥ሴንትራል አፍሪቃ ሪፐብሊክ፥ቻድ፥ደቡብ ሱዳን፥ሶርያ፥ዩክሬን ወዘተ ፡ተጨማሪ ስደትን የቀመሱ
ሐገሮች ናቸው።ነገ ወደስደት እንደማይገባ ማንም ርግጠኛ መሆን አይችልም።እኔ ከጥቅምት ወር 1998ዓ/ም ስደት
በሕይወቴ ውስጥ ይከሰታል ብዬ አስቤ አላውቅም ነበር።ዛሬ ቅልጥ ያልኩ ስደተኛ ሆኜ የኔ ጦስ ለባለቤቴም
ተርፏል።ሃገር አልቦች ሆነናል።
ባለፉት ስድስት አመታት በዩጋንዳ ካምፓላ በተለያዩ ስፍራዎች “የዩኤንኤችሴር” አጋፋሪ በሆነው “ኢንተር ኤድ”
አስተባባሪነት በተከናወኑ የስደተኞች ቀን በዓል ላይ ኮከብ ተሳታፊ ነበርኩ። ዘንድሮም ዕለቱን ማክበሬ የማይቀር
ነው።
በደም የተቋጨው ምርጫ 97 የበርካት ንጹሃንን ደም ገብሮ ካለፈ ዘጠኝ ዓመታት ተቆጥሮአል።ገዳዮቹ ዛሬም ለፍርድ
አልቀረቡም።ሃገሪቱም በከፋ ሁኔታ ላይ ትገኛለች።ጋዜጠኞችና ጦማሪያን በፈጠራ ክስ እስር ቤት ታጉረዋል።
ዴሞክራሲ በገዢዎች መልካም ፈቃድ የምትሰጥ ብርቅ ስጦታ ሆናለች።የስደተኛው ቁጥር እያሻቀብ ነው።እንኳን የኔ ብጤ
ስደተኛው ወደ ትውልድ ሃገሩ ሊመልስ ይቅርና ሃገር ቤት ያሉትም መውጫ አጥተው ያሉበት ሁኔታ ነው ያለው።ሃገር
ቤት።
በመጪው 2007 ዓ/ም በኢትዮጲያ ምድር የሚከናወነውን ብሄራዊ ምርጫ በነጻና ፍትሃዊ መንገድ ለማከናውን ቀድመው
መመቻቸት ያለባቸው ጉዳዮች
እስካሁን መተግበራቸውን እጠራጠራለሁ።
ነጻን ገለልተኛ የምርጫ ቦርድ በአዲስ መልክ አልተዋቀረም።
የሚዲይ በነጻነት የመጠቀም ጉዳይ እልባት አላገኘምም።
ገዢው ቡድን ልቡን ለነጻ ምርጫ ያዘጋጀ ለመሆኑም ከተፈጥሯዊ ባህሪው አኳያ እስካሁን ማረጋገጫ አልሰጠም።
ምርጫውን በአስፈላጊው ዘዴ በመጠቀም ዘላለማዊ ገዢ ለመሆን ይጠቀምበታል እንጂ ለማንም 1 ወንበር ማጋራት
አይፈልግም።የግርማ ሰይፉም በአፓርላማው መኖር ሳያቃጥለው አይቀርም፡
የኔ ስጋት በ2007 ምርጫ ማግስት የከበዱ ሁኔታዎች በሃገሬ ላይ እንደሚከሰቱና የዓለም የስደተኞች ቀን በ2015
ሲከበር የኢትዮጲያዊያን ቁጥር እንደሚያሻቅብ ብገልጽ ማሟረቴ አይሆንም።
ከ1997 ዓ/ም ወዲህ በተፈጠረው ሃገራዊ ቀውስ ምክንያት በርካታ ኢትዮጲያዊያን የፖለቲካ ስደተኞች በኡጋንዳ
የምንኖር ሲሆን ባለፉት 8 ዓመታት “በዩኤንአኤችሴር” ካምፓላና በዩጋንዳ መንግስት ያሉበት የደህንነት ስጋት
ምክንያት ወደ 3 ኛ ሃገር” ሪስትልመንት” አግኝተው የበረሩት “የቶንቦላው ባለዕድሎች” ጥቂቶች ሲሆኑ በርካቶች
አሁንም ደጅ እየጠኑ አሉ።እኔ ደጅ ጥናቴን አላቋረጥኩም።
እኔ ራሴ በቅርበት የማውቃቸው 3 የፖለቲካ ስደተኞች ባለፉት 2 ዓመታት በህመምና ስደቱ ባስከተለባቸው መራራ
ህይወት ተስፋ በመቁረት ወደ አይቀሬው መቃብር ወርደዋል።
3ቱም (UNHCR) ቢሮ ለዘመናት ሲመላለሱ ከርመው የዩጋንዳን አፈር ለብሰው ቀርተዋል።
የኔና የባለቤቴም ጉዳይ ላለፉት 6 ዓመታት ውሳኔ ሳያገኝ በተስፋ ዕድሚያችንን እያቃጠልን ነው።የኔስ የመረጥኩት
መንገድ ስልሆነ ነው።ባለቤቴ ግን ከዱባይ መጥታ ስደተኛ ሆና ያለስራ መጉላላቷ የሚያሳዝን ጉዳይ ነው።
የኔ ሕይወት በኡጋንዳ ምድር ልዩነቱ ሃገር ቤት ከባልደረባዬ እስክንድር ነጋ ጋር ቃሊቲ አለመታሰሬ እንጂ የቁም
እስረኛ ወይም በግዞት እንደሚኖር ሰው ነኝ ብል አልተጋነነም።
ላለፉት 7 ዓመታት በዩጋንዳ ቆይታዬ ገና ለጋ ስደተኛ ሳለሁ የኢትዮጲያን ሚሊኒየም ሲከበር ፕሮግራሙን
ከማስተባበር ጀምሮ በወቅቱ ከወያኔ ቆንስላ ጋር ሚሊኒየሙን በጋር ለማክበር ሲደረግ የነበረውን “መሞዳሞድ”
በመቃውም በዓሉን ወያኔን ባላሳተፈ ሁኔታ በድምቀት እንዲከበር ባደረኩት የጎላ ተሳትፎ “የወያኔ ክልል 16″(
ካምፓላ) ጥቁር መዝገብ ከሰፈሩት “አሸባሪዎች”(ወያኔ ያልተመቹትን ሰዎች የሚለጥፍባቸው ዓለም አቀፍ ታፔላ
ነው)ቁጥር ሁለት መስመር ላይ እንደምገኝ ይታውቃል።
የኢትዮጲያን ማህበረስብ በዩጋንዳ (ethiopian comunity) ከAug,2007 ጀምሮ የበጎ ፈቃድ ተስትፎ
ሳደርግ በመቆየት Nov2010 በተደረገ ጠቅላላ ጉባዔ በቦርድ አባልነት ተመርጬ እስከ አሁን ድረስ በማደርገው
እንቅስቃሴ ያልተደሰቱ ሃይሎች ኮሚኒቲውን ለመቆጣጠር በመፈለግ በሚያደርገው ሴራ አመራሩን ለማዳከም የሚደረገውን
ተግባር በመቃወሜ በጠላትነት ተፈርጄ እንቅስቃሴዬ ስጋት ላይ ወድቋል።
ከጃንዋሪ 2008 ጀምሮ በስደተኛው ህጋዊው ቅዱስ ሲኖዶስ በሚመራው የስደተኞች ቤተክርስትያን የሰበካ ጉባዔ ስራ
አመራር ሆኜ በማገልገል ላይ ስሆን ከጁን 2010 ጀምሮ በተፈጠረው ውዝግብ የጥቃት ዒላማ ሆኜ በርካት መከራ
ደርሶብኛል።ድብደባም ተፈጽሞብኛል።(የካዛንቺስ ልጅ ተደብደቦ ዝም ባይልም ባለኝ ማህበራዊ ሃላፊነት ለሌሎችአርአያ
ለመሆንና መሰናክል ላለመሆን በማንም ላይ ዕጄን አላነሳሁም።ወደፊትም አላነሳም።) በተቀነባበረ ወጥመድም በፈጠራ
ክስ እስከ መታሰርና ዲፖርት ለማስደረግ የተሞከረው ደባ በወገኖቼ ርብርብና በአምላክ ፈቃድ እንደከሸፈ በቂ መረጃ
አለ።
አሁንም ክትትሉና ማወከቡ በመቀጠሉ እንድልቤ ከቦታ ቦታ ለመንቀሳቀስ ተቸግሬያለሁ።
#ለተወሰነ ጊዜ የብሔራዊ ሽግግር ምክር ቤቱ የዩጋንዳ ሪፕረዘንታቲቭ ዲፕሎማት ሆኜ በቆየሁበት ወቅት በጣት
ክሚቆጠሩ ወዳጆቼ በቀር አብሮኝ ሻይ የሚጠጣ ወገን እስከማጣት የደረስኩበትና የፖለቲካ ሰው እስክመስል ድረስ(
በወዳጅም በኢ-ወዳጅም)በፖለቲካ አክቲቪስትነት ተፈርጄ መራራ ወቅቶችን አሳልፌያለሁ።አሳዳጆቼ መውጫ መግቢያ
በማሳጣት ሐገር ለቅቄ እንድጠፋ ቢፈልጉም ሃገር አልባው የትም ልሄድ እንድማልችል ግን አላወቁም።
በየጊዜውችግሬን ለሚመለከታቸው አካላት ባቀርብም ዘላቂ መፍትሄ አላገኘሁም።ውሎዬ በጠላት በተወረረ ፈንጂ ወረዳ ውስጥ ነው።
የተለያዩ ጹሁፎችን” በኢትዮጲያን ሪቪው” ኦን ላይን ላይ ፖስት በማድረግ ሃስብን በነጻነት የመግለጽ ነጻነቴን
ኤክሰርሳይስ ሳደርግ ብቆይም ከዲሴምበር 2013 አጋማሽ በሳውዲ የሚኖሩ ወገኖቻችን ላይ የደረሰውን የሰባዊ መብት
ረገጣ በመቃውም ለዓለም ህብረተሰብ ድምጻችንን ለማሰማት ህዝባዊ ስብሰባ በኮሚኒቲ ደረጃ ለማዘጋጀት በማስተባበሬ
የወያኔ ቆንስላ ለዩጋንዳ መንግስት ደብዳቤ በመጻፍ ፖሊስ ጣቢያ ድረስ ከኮሚኒቲ ለቀመንበራችን አቶ ዘለቀ ጀበሮ
ጋር ተጠርተን ስብሰባውን እንድናቆም በከፍተኛ የፖሊስ ኮማንደሮች ጥብቅ መመርያ ተሰጥቶን ስብሰባውን ለመሰረዝ
ተገደናል።
በጉዳዩ ዙርያ ያማከርኩዋቸው “የሰባዊ መብት ተከራካሪ ድርጅትና” “የኢንተሬድ ሌጋል ኦፊሰር” እንደነገሩኝ
የማደርጋቸውን ተግባራት እንዳቆምና በሃገሬ ዙርያ የምጽፋቸውን ስራዎች ማቆም እንድሚገባ በማስጠንቀቃቸው
“ከኢትዮጲያን ሪቪው” ኦን ላይን ድረ ገጽ ዜናዎችናጹሁፎች ማተሜን አቁሜያለሁ።
አማካሪዎቼ እንዳሉት ሐገር አልባ ስደተኛ በተሰደደበት ሐገርና በስደት በሚኖርበት ሐገር ጉዳይ ላይ መሳተፍ
እንደማይችል ዩጋንዳ በ2006 ያወጣችው “የሪፊውጂ አክት “ይጠቅሳል።
#ሃገር አልባ(stateless)ዝም ማለት አለበት እንደማለት ነው።
ስደተኞች የራሳቸውን ማህበር መመስረት አለባቸው የሚል ሃሳብ ከጥቂት መሰል ወገኖች ጋር ከMar 2013 ጀምሮ
በርካታ ውይይቶች በማድረግና አስተባባሪ ኮሚቴ በማቋቋም የማስታወቅያ ስራዎችን በመስራቴ ካምፓላ
ለኔ የስጋት ስፍራ ሆናለች።
እንደ ጋዜጠኛና ሰባዊ መብት ተሟጋች እየጻፍኩ ለመኖር አስጊ ሁኔታ ላይ መሆኔን ማን ሊረዳልኝ እንደሚገባ ምላሹን
ከአንባቢ እጠብቃልሁ።
በዚህ ሁኔታ ላይ ሆኜ ነው አለማቀፉን የስደተኞች ቀን ኡጋንዳ ላይ ለስድስተኛ ጊዜ ለማክበር በዋዜማ ላይ የምገኘው።
የዘንድሮው የስደተኞች ቀንን ለኔ ልዩ የሚያደርገው “ለዓመታት የደከምንበት “በዩጋንዳ የኢትዮጲያዊያን ስደተኞች
ማህበር በዩጋንዳ”የመመስረት ሂደት በጣት የሚቆጠሩ ቀናት በቀሩበት ሁኔታ በመሆኑ የህሊና ዕርካት እንደተሰማኝ
ለመግለጽ እወዳለሁ።
ዓለማቀፉ የሰባዊ መብትና የጋዜጠኞች መብት ተሟጋች ድርጅቶችና ግለስቦች ለኔና መሰል ስደተኛ ወገኖች ተጨባጭ
የሆነ መፍትሄ ይዘው እንዲቀርቡና( ከሙታን በላይ ከቋሚ በታች ) ከሆነው ሕይወታችን እንዲታደጉን የሁሉ መፍትሄ
ምንጭ በሆነው 1አምላክ ስም ጩኸቴን አሰማለሁ።
በምስራቅ አፍሪካ ያለን ጥቂት ያካባቢው ስደተኛ ጋዜጠኞች በዩጋንዳ ጋዜጠኞች ዩኒየን ቢሮ ከ Dec 2012 ጀምሮ
ለመሰባሰብ ብንሞክርም ሁኔታዎች ባለመመቻቸታቸው እንደባለሙያ የጎላ ተግባራት ባናከናውንም በስም ደረጃ
ተደራጅተናል።
ከላይ ለመግለጽ እንደሞከርኩት የአለም አቀፉ የስደተኞች ቀን ሊከበር ቀናት በቀሩበት ሁኔታ ለኔና ከኔ ጋር
ከSep2007 ጀምሮ የመከራ ሕይወት የምትገፋውና ለኔ ብላ ስደተኛ ለሆነችው ባለቤቴ ምን አዲስ ተስፋ ይዞ
እንደሚመጣ የምናየው ይሆናል።
ፍትህና መፍትሄ ለኛ በ2014 በአምላክ ፈቃድ ይሁን!!!
ደረጀ በጋሻው(penethiopian)
የምስራቅ አፍሪቃ ስደተኛ ጋዜጠኞች ማህበር ሊቀ መንበርና
የኢትዮጲያ ማህበረሰብ በዩጋንዳ ማህበራዊ ጉዳይ ተጠሪ
ካምፓላ ኡጋንዳ
ሰኔ 11ቀን 2006 ዓ/ም(June 18,2014)
እግዚአብሄር አምላክ የስደትና የመከራ ዘመኔን መፍትሄ ይስጠው።
+256782302124

Viewing all 15006 articles
Browse latest View live