Quantcast
Channel: Ethiopian News | ዘ-ሐበሻ | Latest News Provider | News For All
Viewing all 15006 articles
Browse latest View live

ለምን የሳሙኤል ዘሚካኤል ጉዳይ ያን ያህል ያስደንቀናል? (በትረ ያዕቆብ)

$
0
0

ከበትረ ያዕቆብ

በትረ ያዕቆብ

በትረ ያዕቆብ

ሰሞኑን በማህበራዊ ድረ ገፆች አካባቢ የህዝብን ቀልብ መሳብ የቻለና አሁንም ዋና መወያያ አጀንዳ ሆኖ የቀጠለ ጉዳይ ተከስቷል፡ የሳሙኤልዘሚካኤልየሀሰትዶክተር እናኢንጂነርነት፡፡ ጉዳዩ ብዙዎችን አጃኢብ አስብሏል ፤ አሁን በርካቶች ብስጭታቸዉን እና ቁጣቸዉን በተለያየ መንገድ እየገለፁ ይገኛል፡፡ ብዙ ሰዎች በአንድ ወቅት የስኬት ምልክታቸዉ እስከ መሆን የደረሰና አድናቆታቸዉን ያጎረፉለት ሰዉ ድንገት የሀሰት ሆኖ ሲያገኙት መደናገጣቸዉ አልቀረም፡፡

እርግጥ ነዉ ነገሩ ትንሽ የሚያስገርም ነዉ፡፡ ወጣቱ የሄደበት እርቀት ግራ የሚያጋባና ድፍረቱ የሚያስገርም ነዉ፡፡ ሌላዉን ትተን በሀገር ዉስጥ የሚገኙትን ዩንቨርሲቲዎች ስም ደጋግሞ እያነሳ ይህንን ሸለሙኝ ፣ ይህንን ሰጡኝ ፣ የረዳት ፐሮፌሰርነት ማዕረግ ተበረከተልኝ ወዘተ ማለቱ በእርግጥም ከማሰገረም አልፎ ብዙ ያስብላል፡፡ ያም ሆኖ ግን እኔን ይበልጥ ያስገረመኝ ጉዳዩ የዚያን ያልህ  እንደ ተዓምር የመታየቱ ነገር ነዉ፡፡ በጉዳዩ ዙሪያ እየተደረገ ያለዉን ዉይይት ስመለከት እንዴ ነዉ ነገሩ ብየ መደነቄ አልቀረም፡፡

በዚህ ወጣት የተፈፀመዉ አሳፋሪ ተግባር ዛሬ የተከሰተ አዲስ ክስተት አይደለም ፤ የነበረና አሁንም  እየተፈፀመ ያለ ነገር ነዉ፡፡  እዉነቱን መነጋገር ካለብን መሰል ማጭበርበር ቤተ-መንግስት አካባቢ በጣም የተለመደ እና  ብዙዎች የተጨማለቁበት ተግባር ነዉ፡፡ ይታያችሁ ፣ ቤተ-መንግስት ነዉ ያልኩት፡፡ ይህንን ስናይ ወጣቱ የፈፀመዉ ተግባር የሚደንቅ አይመስለኝም፡፡ እንዴትስ ያስደንቃል፡፡

ዛሬ ሳሙኤልዘሚካኤልእድል ጥሎት ሁሉም ተረባረበበት እንጅ የኢህአዴግ ባለስልጣናት የትምህርት ማስረጃ ቢመረመር ስንት ከሱ የባሰ ጉድ ይገኝ ነበር፡፡ እንግዲህ ሀገርን ያህል ትልቅ ነገር እንመራለን የሚሉ  ግለሰቦች መሰል ተግባር በሚፈፅሙበት አገር የዚያ ወጣት ተግባር ጉድ የሚያስብልበት ምክንያት አይታየኝም፤፤ እንዴትስ ሊያስብል ይችላል፡፡ ከዚህ ይልቅ ቤተ-መንግስት ተቀምጠዉ አገርን የሚዘዉሩ ግለሰቦች ፣ በያንዳንዳችን እጣ ፈናታ ላይ የመወሰን ስልጣን በጉልበት የጨበጡ ባለስላጣናት የሀሰት ማስረጃ ሊያስደንቀን ፣ ሊያበሳጨን ፣ ሊያስደነግጠን ይገባ ነበር፡፡

ዛሬ በርካታ የኢህአዴግ/ህወሀት ጉምቱ ባለስልጣናት እንከዋን ትምህርት ቤት ገብተዉ ሊማሩ በበሩ እንኳን ሳይልፉ ባለሁለተኛ እና ሶስተኛ ድግሪ የመሆናቸዉ ጉዳይ ለብዙዎቻችን ሚስጥር አይመስለኝም፡፡ ዛሬ የአዲስ አበባ ዩንቨርሲት ድግሪና ማስትሬት በቀጭን ትእዛዝ እንዳሻቸዉ የሚሰበስቡት ተራ ነገር ነዉ፡፡ ሲያሻቸዉም ከዉጭ በገንዘብ ይሸምቱታል፡፡ ሲልም እድሜ በሙያዉ ለተካኑ የቻይና እና የህንድ ዜጎች እንደፈለጉት አሳምረዉ አዘጋጅተዉ ኮንግራ ይሏቸዋል፡፡ከዛም ከለታት አንድ ቀን ብቅ ብለዉ ይህ አለን ይላሉ፡፡ ይህ ነዉ ለኔ አሳፋሪዉ ፣ አስደንጋጩ፡፡

በእንዲህ አይነት መልኩ በርካታ ትልልቅ ባለስልጣናት የሀሰት የክብር ካባ ለመደረብ ሞክረዋል፡፡ አሁንም ብዙዎች ይህንን መንገድ ቀጥለዉበታል፡፡ ከብዙ ወራት በፊት አንድ አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ዉስጥ የሚሰራ ወዳጄ ሲያጫዉተኝ “ዩንቨርስቲዉ በካድሬ መመራት ከጀመረበት እለት አንስቶ በርካታ የኢህአዴግ መኳንንቶችን በማዕረግ” አመርቋል” ነበር ያለኝ፡፡ ይታያችሁ እርሱ ያለዉ “በማዕረግ” ነዉ፡፡ ይህ ማለት ሳይማሩ ፣ ሳያጠኑ ፣ ሳይፈተኑ ኤ በ ኤ ይሆናሉ ማለት፡፡ ለኔ ይሄ ነዉ አስደንጋጩ ጉዳችን፡፡ ይህ ወዳጄ እንደነገረኝ አልፎ አልፎም በዉጭ ዩኒቨርስቲ መማር የሚፈልጉ ከተገኙም የሚፈልጉትን የትምህርት መስክ መርጠዉ የመዓረግ ተመራቂ ተብሎና ሁሉም ነገር ተሟልቶለት ይሰጣቸዋል፡፡ እኒህ ሰዎች ናቸዉ ዛሬ ሀገሪቱን የሚመሩት ፤ ከእኛ በላይ አዋቂ የለም የሚሉን ፣ የጭቆና ቀምበር ጭነዉ ፍዳችንን የሚያሳዩን፡፡

ከዚህ ጋር በተያያዘ ሁለት ግለሰቦች ማንሳት እዉዳለሁ፡፡ ይህ ለምሳሌ ያህል ብቻ ነዉ፡፡ የመጀመሪያዉ በአንድ ወቅት እንደ ምሁር ለመፈላሰፍ ሲቃጣዉ የነበረዉ የቀድሞዉ ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ መለስ ዜናዊ ነዉ፡፡ ሰዉየዉ ትምህርቱን ከዩንቨርሲቲ አቋርጦ በረሀ እንደ ወረደ እና ከ17 አመት የትጥቅ ትግል በኋላ በለስ ቀንቶት ቤተ-መንግስት እንደገባ ነዉ ነበር የምናዉቀዉ፡፡ ሆኖም ከእለታት በአንዱ ቀን አቶ ምን ይሳነዋል ባለሁተኛ ድግሪ ምሁር ነዉ ሲባል ሰማን ፣ ያም አልበቃ ብሎ ሌላም እንዳከሉበት የቀብሩ እለት ተነገረን፡፡ የአቶ ሳሞራ የኑስም ታሪክ ተመሳሳይ ነዉ፡፡ 11ኛ ክፍል አቅርጠዉ በረሀ ገብተዉ እንደታገሉ እንጅ ሌላ የምናዉቀዉ ነገር አልነበረም፡፡ ሆኖም  እርሳቸዉ ከ11 ክፍል በአቋራጭ ከፈለጉት ቦታ ላይ ጉብ አሉ፡፡ በሀዉልታቸዉ ላይም ባለ ሁለተኛ ድግር ምሁራ ናቸዉ ተብሎ ተፃፈ፡፡ እንዴት ብሎ የጠየቀም አልነበረም፡፡ እስከማዉቀዉ ድረስ በጉዳዮ ላይ ጥያቄ ያነሳ ብቸኛ ሰዉ ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ብቻ ነዉ፡፡ ዛሬ “ለእዉነት ቆሜያለሁ” የሚለዉ ሬድዮ ፋናም ያኔ አዳች ነገር ትንፍስ አላለም ነበር፡፡ ይህ ብቻ አይደለም በቅርቡ ብዙ አፍሪካዊ ጋዜጠኞች  የተሳለቁበት በሀሰት የትምህርት ማሰረጃ በመንግስት ሴራ የአፍሪካ ህብረት አካል በሆነ ድርጅት ዉስጥ ትልቅ ስልጣን እስከመጨበጥ የበቃዉ የኢህአዴግ ካድሬም በምሳሌነት ሊጠቀስ ይችላል፡፡

እንግዲህ ይታያችሁ እነዚህ ሰዎች ሀገር መሪ ነን ይላሉ፡፡ እነዚህ ናቸዉ የሀገሪቱን ፖሊሲና እስትራቴጅ ቀራፂያን ፣ እነዚህ ናቸዉ ሀገሪቱ እና እኛን ወክለዉ ከሌሎች ጋር የሚደራደሩት ፣ እነዚህ ናቸዉ ዛሬ በእያንዳንዳችን ህልዉን ላይ ወሳኝ ሆነዉን የሚገኙት፡፡ ይህ ነዉ እኔን ይበልጥ የሚያሳፍረኝ ፣ የሚያሰገርመኝ፡፡ ይህ ነዉ ለኔ ትልቁ ጉድ፡፡ እንዴት ነዉ እንዲህ አይነት የሀገር መሪዎች ባሉበት ሀገር አንድ ከደሀ ቤተሰብ የወጣ ልጅ የፈፀመዉ የማጭበርበር ተግባር የሚደንቀዉ፡፡ ነዉ ወይስ አላዉቅም ልንል ነዉ፡፡

ከባለስላጣናቶቻችን እና ከእኛ ዜጎች አልፎ ተርፎ እንኳ በየዩንቨርስቲዉ በዶክተር እና ፕሮፌሰርነት ማዕረግ ስም የሚያጭበረብሩት የዉጭ ዜጎች በርካታ አይደሉም? የመጀመሪያ ድግሪ ይዘዉ በዶክተር ስም የነገ ሀገር ተረካቢ በሆኑ ወጣት ልጆች ላይ ሲቀልዱ አላየንም ፣ አልሰማንም ? ለምሳሌ እንኳን በቅርቡ ወደ አንድ የዉጭ ዩንቨርስቲ  ሁለተኛ ድግሪዉን ለመማር ያቀና ወጣት ዶክተር ነኝ ብሎ ካስተማረዉ የዩንቨርሲቲ መምህሩ ጋር በአንድ ክፍል ዉስጥ ለትምህርት እንደተገናኙ ሲተረክ ሰምተናል፡፡

በጥቅሉ እንነጋገር ከተባለ በርካታ ጉድ በዙሪያችን አለ፡፡ ዘርዝረን አንጨርሰዉም፡፡ በመሀከላችን በርካታ የቀበሮ ባህታዊያን እንዳሉ ልብ ልንል ያገባል፡፡ ይህ እየሆነ ባለበት አገር የሳሙኤልተግባር ለኔ ብዙ የሚያስደንቅ ነዉ ብየ አላስብም፡፡ እንዴዉም በአንድ ግለሰብ የማጭበርብር ተግባር ላይ ብቻ ማፍጠጡ ችግሩ እንደሌለ ያስመስለዋል ፤ ወደ መፍትሄም አይወስድም፡፡ ስለዚህም ችግሩን ሰፋ አድርጎ ማየትና አፍረጥርጦ መነጋገር ተገቢ ነዉ እላለሁ፡፡ ሬድዮ ፋናም ቢሆን “ለእዉነት ቆሜያለሁ” የሚል ከሆነ በአንድ ግለሰብ ተግባር ላይ ብቻ ከማንባረቅ በዘለለ የሌሎችንም በተለይም ሀገር እንመራለን በሚሉ የኢህአዴግ/ህወሀት አምባገነን ባለስልጣናት እየተፈፀሙ ያሉ ማጭበርበሮችን ሊያጋልጥ ይገባል፡፡ እርግጥ ኢህአዴግ አምጦ ከወለደዉ ተቋም ይህን መጠበቅ ሞኝነት ነዉ፡፡ ለሁሉም ቸር እንሰንብት !


‹‹የኢትዮጵያን ወጣቶች የጨፈጨፉትን በህግ የምንበቀልበት ጊዜ ይመጣል›› –ዶ/ር ያዕቆብ ኃ/ማርያም

$
0
0

Dr_Yacobወጣቶች በአልሞ ተኳሽ ግንባራቸው ሲበረቀስና ልባቸውን ሲመቱ ስናስታውስ እንባ ያልተናነቀው ያለ አይመስለኝም፡፡ እነዚህ እውነተኛ መስዋዕትነት የከፈሉ ወጣቶች ደመከልብ ሆነው እንዳይቀሩ ኃላፊነቱ የእኛ ነው፡፡ የእነሱን ደም ልንበቀል የምንችለው የቆሙለትን አላማ እውን ስናደርግ ነው፡፡ ይህንን አላማ እውን ስናደርግ እንደ ሞቱም ላይቆጠር ይችላል፡፡ ሌላኛው የምንበቀልበት መንገድ ደግሞ ህግን በመንተራስ ነው፡፡ በአገራችን ባለስልጣናት በየጊዜው ወንጀል እየፈጸሙ፣ በወንጀል እየተነከሩ፣ ምንም ተጠያቂነት ሳይኖርባቸው ለብዙ ጊዜ ታልፈዋል፡፡ በአገራችን ባለስልጣናት ለፈጸሙት ወንጀል ተጠያቂ ያለመሆን ባህል በሰፊው የተስፋፋ ነው፡፡

አሁንም ቢሆን ይህን ባህል መስበር ይኖርብናል፡፡ እያንዳንዱ ሰው ለሰራው ወንጀል ተጠያቂ መሆን አለበት፡፡ በተለይ ባለስልጣናት ከባድ ከባድ ወንጀል እየሰሩ በነጻነት ሳይጠየቁ የሚያልፉበት ጊዜ አለ፡፡ ይህ በእውነት መታረም ያለበት ነገር ነው፡፡ ለሰሩት ወንጀል ተጠያቂነት መኖር አለበት፡፡ በዛ አይነት ነው ወንጀል እንዳይፈጸም ልንገታው የምንችለው፡፡ አንድ ሰው በሰራው ወንጀል ተጠይቆበት ከተቀጣ ለሌላው ማስተማሪያና ምሳሌ ይሆናል፡፡ አሁንም ቢሆን እነዚህ ወጣቶችን ግንባር ግንባራቸውንና ልባቸውን ተኩሰው መትተው የገደሉ ሰዎች ከተጠያቂነት አይድኑም፡፡ ከ70 አመት በፊት በናዚ ዘመን በግፍ ሰው የጨፈጨፉ በቅርብ ጊዜ እስፔን ውስጥ ተይዘው ክስ ቀርቦባቸዋል፡፡ የኢትዮጵያን ወጣቶች የጨፈጨፉትንም በህግ የምንበቀልበት ጊዜ ይመጣል ብዬ አስባለሁ፡፡ ማናችንም ብንሆን ከልባችን የምናወጣው ነገር መሆን የለበትም፡፡ እኔ እንደ ህግ ባለሙያ ይህን ጉዳይ ባመቼ ጊዜ ለማንሳት ቃል እገባለሁ፡፡

የጀኔራሎቹ የጓዳ ሽኩቻ! –ቀጣዩ ኢታማዦር ማን ነው?

$
0
0

‹‹ደመወዝ አነሰኝ ብሎ ጭማሪ የሚጠይቅ ካለ አሁንኑ ከሰራዊቱ መልቀቅ ይችላል፡፡›› ይህ የጦር ኃይሎች ኢታማዦር ሹም የሆነው ጀኔራል ሳሞራ የኑስ ሁለተኛው የሰራዊት ቀን በተከበረበት ሰሞን ባህር ዳር ከተማ ሙሉዓለም አዳራሽ ከተሰበሰቡት የሰራዊቱ አባላት መካከል የደመወዝ ጭማሪን በተ
መለከተ ለተነሳለት ጥያቄ ምላሽ ሲሰጥ የተናገረው ነው፡፡

ኢትዮጵያ ከአጼ ኃይለስላሴ ዘመነ መንግስት ጀምሮ ዘመናዊ ውትድርናና የጦር ስልት ሰልጣኝ ወታደሮችንና መኮንኖችን በተደራጀ ስልጠና ማፍራት መጀመሯ ይጠቀሳል፡፡ በሀረርና ሆለታ የጦር አካዳሚዎች በመታገዝ ዘመናዊ የውትድርና ሳይንስ ትምህርት መሰጠት የተጀመረው በዚሁ በንጉሱ ዘመን ነበር፡፡ በዚህ መልኩ እየተደራጀ የመጣው የሀገሪቱ ሰራዊት እስከ ኢህአዴግ ወደ ስልጣን መምጣት ዘመን ድረስ የሀገሪቱ ብሄራዊ ሰራዊት ሆኖ ለመዝለቅ ችሏል፡፡ ሆኖም የደርግ ውድቀትን ተከትሎ በነበረው ጊዜ አያሌ የሰራዊቱ አባላት ለስደትና ሞት እንዲሁም ለብተና ለመዳረግ በቅተዋል፡፡
millitery ethiopian
(በእርግጥ ቀደም ብለው የተማረኩትን የቀድሞው የሰራዊቱ አባላት በኢህአዴግ ውስጥ ማግኘት እንደሚቻል ኩማ ደመቅሳ (የፖሊስ መቶ አለቃ እነደነበር ይነገርለታል)፣ እና ተራ ሚሊሻ እንደነበር የሚነገርለት አቶ አባዱላ ገመዳን ከፊት መስመር ላይ በማስቀመጥ መጥቀስ ይቻል ይሆናል፡፡ እንደነዚህ ያሉት የቀድሞው ሰራዊት አባላት ደርግ ከመውደቁ በፊት ከድተው የህወሓትንና የኢህዴንን ታጋዮች የተቀላቀሉት ናቸው፡፡)

እናም በጊዜው ታጋዮች ሀገሪቱን በሙሉ ለመቆጣጠር መቻላቸውን ተከትሎ የኢትዮጵያ ሰራዊት (የደርግ ሰራዊት ብቻ ብሎ ማቃለሉን አልፈለግሁትም) ሜዳ ላይ ተበትኖ እንደቀረ ይታወሳል፡፡ ስለሆነም የኢህአዴግ ሰራዊት ሲያሸንፍ ሊያስተምሩት የሚችሉ አንዳንድ የቀድሞው ሰራዊት አባላት መኮንኖችን ብቻ አስቀርቶ ሌላውን ወደጎን ገፍቶታል፡፡ በተለይም የኢትዮጵያ የባህር ኃይል ሙሉ ለሙሉ ሲፈርስ ያለቀው ሰራዊት አልቆ በዚያው የሸሸውም የመን ላይ ለእስር ተዳርጎ ከፍተኛ ስቃይ መጋፈጡ የአደባባይ እውነት ሆኖ ተመዝግቦ ይገኛል፡፡ በዚህም ኢትዮጵያ አሁን ላይ ያለ አንዳች ባህር ኃይል፣ ያለ አንዳች የተፈጥሮ የባህር በር የቀረች ሀገር ለመሆን ተዳርጋለች፡፡ አሁን ያለው መከላከያ ሰራዊታችን የምድርና የአየር ኃይልን ብቻ ያቀፈ ነው፡፡ የምድር ኃይሉ ሙሉ ለሙሉ ለማለት በሚያስደፍር ሁኔታ በቀድሞ ታጋዮችና በቅርብ ጊዜ ምልምሎች የተደራጀ እንደሆነ ሲነገርለት፣ አየር ኃይሉ ላይ ግን ኢህአዴግ እንደገባ የአየር ኃይል ሳይንስን እንዲያስተምሩት የመረጣቸውን ጥቂት የቀድሞው የኢትዮጵያ ሰራዊት አባላትን በውስጡ የኋላ ደጀን አድርጎ ይዞ መቆየቱ ይነገራል፡፡

በአጠቃላይ ህወሓት/ኢህአዴግ ደርግን አሸንፎ ስልጣን ላይ እንደወጣ በትግል ይዞት የመጣውን ሰራዊት ‹‹ብሄራዊ ሰራዊት›› ለማድረግ ችሏል፤ ወዲያውም እዙ በመለስ ዜናዊ ስር እንዲሆን መደረጉ ታወቀ፡፡ ኢህአዴግ እንደገባ አካባቢ ብዙ ሰዎች ሰራዊቱን ‹የገበሬ ሰራዊት› እያሉ ይጠሩት እንደነበር
ይታወሳል፡፡ በሂደት ግን ቀድሞ የነበሩትንና ሌሎች አዳዲስ የወታደራዊ ትምህርት ቤቶችን በመጠቀም ሰራዊቱን የማዘመን ስራ ተሰርቷል፤ አዳዲስ የሰራዊቱ አባላትን በአዲስ ዘመናዊ ስልጠና ኮትኩቶ ወደሰራዊቱ ማካተት ተችሏል፡፡ አሁን ላይ የኢትዮጵያ ሰራዊት ልክ እንደ አያቶቹና አባቶቹ ሁሉ ግዳጁን
በብቃት የመወጣት ተፈጥሮአዊ የጀግንነትና የግዳጅ ስብዕናን የተላበሰ እንደሆነ ብዙዎች ምስክርነታቸውን ይሰጡታል፡፡ በእርግጥም የሰራዊቱ ጀግንነት ሊካድ የሚችል አይደለም፤ ሀቅ ነውና፡፡ አንዱ ማሳያ የሚሆነንም በተለያዩ ዓለም አቀፍ የሰላም ማስከበር ግዳጆች ላይ አመኔታን አትርፎ በመመረጥ በተ
ሰማራበት ግንባር ሁሉ በሚገባ ግዳጁን ለመወጣት መቻሉ ነው፡፡

አሁን ያለው ሰራዊት በአዲስ መልክ ‹ብሄራዊ ሰራዊት› ሆኖ በአዋጅ የተደራጀው የካቲት 7/1988 ዓ.ም እንደነበር ይታወሳል፡፡ (ይህን ቀን ከዛሬ ሁለት ዓመት በፊት ጀምሮ የሰራዊት ቀን በሚል ሰራዊቱ እንዲያከብረው ተወስኖ ሁለት ጊዜ ለማክበር ችሏል፤ የአድዋ ድል የተመዘገበበት ታሪካዊ ቀን እያለ ይህኛው እንዴት ‹‹የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ቀን›› ተብሎ እንደተመረጠ አወዛጋቢ ቢሆንም ቅሉ!) ለማነኛውም በማደራጃ አዋጁ ላይ የመከላከያ ሰራዊቱን ግዳጅና ‹የማንነት› ተዋጽኦ በአጭሩ ለመግለጽ ተሞክሯል፤ ‹‹የሐገሪቱን ሉዓላዊነት የሚያስከብር፣ የኢትዮጵያን ብሔር ብሔረሰቦች ሚዛናዊ ተዋጽኦ ያካተተ፣ ከማናቸውም ፖለቲካ ድርጅት ወገንተኝነት ነጻ በሆነ ሁኔታ ተግባሩን የሚያከናውን ሰራዊት ማደራጀት…›› በሚል፡፡

ቃል የሚዋሸከው እንግዲህ እዚህ ጀምሮ ነው፡፡ ‹‹ሚዛናዊ ተዋጽኦ›› እና ‹‹ከማናቸውም ፖለቲካ ድርጅት ወገንተኝነት ነጻ…›› የሚሉትን ሀረጎች ወስደን ተግባር ላይ ያለውን ስናይ እውነታው ለየቅል መሆኑን እንገነዘባለን፡፡ በመጀመሪያ ደረጃ ኢህአዴግ ነባሩን የኢትዮጵያ ሰራዊት አፍርሶ በምትኩ ተሸክሞ ይዞት የመጣውንና ለስልጣኑ ያበቃውን ሰራዊት ‹ብሄራዊ ሰራዊት› ነው ሲል ወገንተኛነቱ እንደምን ያለ ሊሆን እንደሚችል ቀድሞ የሚያውቀው ጉዳይ ይሆናል፡፡ ሲቀጥል ደግሞ ካሉት አጠቃላይ የሐገሪቱ የጦር ጀኔራሎች መካከል ስንቶቹ የህወሓት ቀኝ እጅ እንደሆኑ ከኢህአዴግም ሆነ ኢትዮጵያ ህዝብ የተሰወሩ አለመሆናቸውን ኢህአዴግ ሊያጣው የሚችለው እውነታ አይደለም፡፡

እስካሁን ከነበሩትና አሁን ካለው የመከላከያ ሰራዊቱ ኢታማዦር ሹሞች መካከል ስንቶቹ የህወሓት እንደሆኑስ የማያውቅ ማን ነው? በእርግጥ አሁን ላይ በጣም አስቸጋሪ በሚባሉ የጦር ግዳጆች ላይ የትኞቹ የሰራዊቱ ክፍሎች በቀዳሚነት እንደሚመደቡ ይታወቃል፡፡ በመከላከያ ሰራዊት ኢንዶክትሪኔሽን ክፍል ውስጥ የሚሰራ አንድ ባለማዕረግ የሰራዊቱ አባል ስለዚህ ሁኔታ ሲገልጽ፣ ‹‹ያስፈልገኛል የምትለውን መሰረታዊ ነገር ለማግኘት እንኳ በጣም አዳጋች ነው፡፡ ሌላው ቢቀር በተለያዩ የሀገሪቱ የልማት ፕሮጀክቶች ላይ ጥበቃ የሚያደርጉ በረሃ አካባቢ ያሉ የሰራዊቱ አባላት ምን አይነት የግዳጅ ሁኔታ ላይ እንዳሉ የሚያውቀው ያውቀዋል፡፡ ስለሰራዊቱ ብዙ መናገር አይቻልም እንጂ ስንት ነገር አለ መሰለህ? አድራጊ ፈጣሪዎቹ ግን እዚህ አዲስ አበባ ላይ ያሉት ሰዎች ናቸው፡፡ ምደባው ጎጠኝነትና ጎሰኝነትንም እንደ ስውር መስፈርት ያስቀመጠ ነው፡፡›› ይላል፡፡በእርግጥ የእነዚህ በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ሆነው ግዳጃቸውን የሚወጡ የሰራዊቱ አባላት ሁኔታ እዚህ መሀል ሀገርና አንጻራዊ ሰላም ባለበት ቦታ ላለነው ኢትዮጵያውያን በግልጽ ባይታየንም፣ በከፍተኛ የሀገርና የወገን ፍቅር ስሜት ሆነው ግዳጃቸውን ስለሚወጡ ግን ምስጋና ይገባቸዋል፡፡ የእነዚህ ቆራጥ ወገኖቻችን ጥረት ነው ሀገርንና ህዝብን የሚ
ያስከብረው፡፡ ዳሩ ግን እንዲህም ሆነው ግዳጃቸውን ሲፈጽሙ ትንሽ እንኳ የደመወዝና የጥቅማጥቅም ጥያቄ ሲያነሱ፣ ‹‹ደመወዝ አነሰኝ ብሎ ጭማሪ የሚጠይቅ ካለ አሁንኑ ከሰራዊቱ መልቀቅ ይችላል፡፡›› የሚል አግባብ ያልሆነና አሳፋሪ መልስ ይሰጣቸዋል፡፡ ይህን መሰሉን መልስ የሚሰጡት ጀኔራሎች እዚህ አዲስ አበባ ላይ የተንደላቀቀ ኑሮ እየኖሩ፣ ምንጩ ያልታወቀ ሀብት እያፈሩ መሆኑ ደግሞ ግርምትን የሚያጭር ነው፡፡

አሁን አሁን ጄኔራሎቻችን የብዙ ኃብት ባለቤቶች እንደሆኑ ይነገራል፤ ይህ ፎቅ የጀኔራል እገሌ ነው፣ ያኛው ደግሞ የጀኔራል እገሌ ነው የሚሉ በርካቶች ናቸው፡፡ ለመሆኑ እነዚህ ጀኔራሎች ገቢያቸው ምን ያህል ነው ብለን ስንጠይቅ ግን ምላሽ አናገኝም፤ ገቢያቸው ይሆናል ብለን ከምናምነው ጋር ለማገናዘብ ከሞከርን ደግሞ ሰዎቹ ሙስና ውስጥ መዘፈቃቸውን ለመናገር እንደፍራለን፡፡ (በነገራችን ላይ የኢትዮጵያ ኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት መስሪያ ቤት ኃላፊ ተደርጎ የተሾመው ሰው ራሱን ከሙስና ያራቀ እንደሆነ የሚነገርለት ሲሆን በሌሎች ሰዎች ላይ ያለውን አሰራር በቅርበት እየተከታተለ እንደሆነ ምንጮች ያነሳሉ፡፡ ‹‹ተውአቸው የሰሩትን ፎቅ ይስሩ፤ በባንክም የሚያስቀምጡትን ያህል ያስቀምጡ፤ በቅርብ ጊዜ ግን ሀብቱ ለሚመለከተው የኢትዮጵያ ህዝብ ይመለሳል›› በማለት መናገሩንም የሚያስታውሱ አሉ፡፡ ይህን የሰውየውን ባህርይ ያጤኑት አንዳንድ ጀኔራሎችና ባለስልጣናት ታዲያ ሰውዬውን ከሙስናና ሌሎች ተያያዥ ጉዳዮች ጋር ለማነካካት ሙከራ ማድረጋቸው አልቀረም፤ እስካሁን እየተሳካላቸው እንዳልሆነ ቢነገርም ቅሉ፡፡) ዝሆኖቹ ጀኔራሎች ይህ ሁሉ ነገር አያሳስባቸውም፤ ተቆጭም ያላቸው አይመስሉም፡፡ እነሱን የሚያሳስባቸው በመካከላቸው ያለውና ሊኖር የሚገባው የእርስ
በእርስ የበላይነት ነው፤ በስልጣንም በሀብትም፡፡ ባለ አራት ኮከብ ጀኔራሉ ሳሞራ የኑስ በመለስ ዜናዊ ምርጫ የጦር ኃይሎች ኢታማዦር ሹም ተደርጎ የተሾመው የዛሬ ሰባት አመት ገደማ እንደነበር ይታወሳል፡፡ (የመጀመሪያው ባለ ሙሉ ጀኔራል ማዕረግ ያገኘ በሚል ምስሉ ብሄራዊ ሙዚየም የተቀመጠለት የጦር ሰው ሳሞራ የኑስ ነው፡፡) ይህ ሰው እስካሁን በስልጣን ላይ ለመቀመጡ ዋነኛ ምክንያት የሚባለው ለመለስ ዜናዊ የነበረው ቅርበትና ታዛዥነት ነው፡፡ በእርግጥ ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ሞት ባይቀድመው ኖሮ ሳሞራን ከኢታማዦርነቱ የማንሳት እቅድ እንደነበረው ይነገራል፡፡

ይህንን ጠንቅቆ ያውቅ የነበረው ጀኔራል ሳሞራ ታዲያ የሚሻርበትን ቀን ሲጠብቅ መለስ ህይወቱ በማለፉ በያዘው ቦታ ለመደላደል ስራዎችን መስራት እንደጀመረ ይወሳል፡፡በመለስ ዜናዊ እቅድ ውስጥ ሳሞራን እንዲተካው ተዘጋጅቶ የነበረው ደግሞ ሳሞራ የሙሉ ጀኔራልነት ማዕረግ ሲደፋለት በሁለተኛነት ደረጃ የሌትናት ጀኔራልነት ማዕረግን የተጎናጸፈው የ‹ብአዴኑ› ወጣቱ የጦር ሰው አበባው ታደሰ ነበር፡፡ ይህን የአበባው ወደ ኢታማዦር ሹምነት መምጣትን አጥብቀው ከማይፈልጉት ሰዎች ደግሞ ጀኔራል ሳሞራ ዋነኛው እንደሆነ ይነገራል፡፡ በዚህም የተነሳ የመለስን ህልፈት ተጠቅሞ ሳሞራ አበባውን ከሰራዊቱ የማግለል ስራ እንደሰራ የሚጠቅሱ አልጠፉም፡፡ እናም የማዕከላዊ እዝ ዋና አዛዥ የነበረውን ሌትናንት ጀኔራል አበባው ታደሰን በቦታው መቆየት ሳሞራ የፈለገው አይመስልም፡፡ አበባው ከማዕከላዊ እዝ አዛዥነት እንዲነሳ ተደረገ፡፡ ይህም ብቻ ሳይሆን ለሳሞራ እምብዛም ቅርብ እንዳልሆነ የሚነገርለትን ሌላው ‹ጠንካራ› ሰው ሌትናንት ጀኔራል ሳዕረ መኮንን (የሰሜን እዝ ዋና አዛዥ የነበረ) ከኃላፊነቱ እንዲነሳ ተደረገ፡፡ አሁን ጀኔራል ሳሞራ ስጋቶቹን ያቃለለ መሰለ፡፡

ሂደቱ በዚህም የሚያበቃ እንዳልሆነ ነው ምንጮች የሚጠቁሙት፡፡ በተለይም በሌትናት አበባው ታደሰ ላይ ያለው ስጋት እሱን ከኃላፊነት በማንሳት ብቻ የሚያበቃ አልሆነም፡፡ በማዕከላዊ እዝና በሌሎችም በሰራዊቱ ከፍተኛ ተቀባይነት እንዳለው የሚነገርለት በእድሜ ትንሹ ጀኔራል አበባው ታደሰ ኃላፊነቱ ከተነሳም በኋላ ከፍተኛ ክትትል እንደሚደረግበት ነው የሚነገረው፡፡ በተለይም ከሰራዊቱ ከአዛዥነቱ ከተነሳ በኋላ ምዕራብ ጎጃም አዊ ከሁለት ሲቪሎች ጋር አንድ ሻይ ቤት እንደታዬ መነገሩ ከፍተኛ ጥርጣሬ እንዲነሳበት አስችሎአል፡፡ ይህን ተከትሎ በማዕከላዊ እዝ ሲደረግ በነበረው ግምገማ ወቅት አንዳንድ የሰራዊቱ አባላትን በጎጠኝነት ሰበብ የማደናገር ሁኔታ እንደታዬ ይጠቀሳል፡፡ አንዳንዶች በግልጽ ‹‹የአበባው አሽከር ነበርኩ ብለህ ሂስህን ዋጥ!›› እየተባሉ እንደተገመገሙ ምንጮች ያወሳሉ፡፡

በእርግጥም አሁን ጀኔራል ሳሞራ ጡረታ የሚወጣበትን ጊዜ በሚገባ ያራዘመ ይመስላል፤ ስጋት ያላቸውን ሰዎችም ከቁልፍ ቦታቸው ለማሸሽ ችሏል፡፡ በመከላከያ ሰራዊት ደንብ መሰረት ቅድሚያነትና ብቃት (ሲኔሪቲ) ትልቅ ተጽዕኖ አላቸው፡፡ ይህን ካየን ደግሞ አሁን ላይ ሰራዊቱ ውስጥ ካሉ ጀኔራሎች መካከል የሳሞራ ምትክ ሊሆን የሚችለው በቀዳሚነት ከሳሞራ አንድ ደራጃ ወረድ ብሎ የሚገኘውና ከሌሎቹ ቀደም ብሎ ሌትናት ጀኔራልነትን ያገኘው አበባው ታደሰ ነበር፡፡ ይህ እንዲሆን ያልፈለገው ሳሞራ ግን ሰውዬውን ገለል ማድረጉን መርጧል፡፡ ሳዕረንም እንዲሁ፡፡ መረጃዎች እንደሚጠቁሙት ጀኔራል ሳሞራ እንዲተካው የሚፈልገው አሁን በአብዬ የሰላም ማስከበር ግዳጅን በአዛዥነት የሚመራው ሌትናት ጀኔራል ዮሃንስ ገብረመስቀል ነው፡፡ ይህ ሰው ሌትናት ጀኔራልነቱን ያገኘው በቅርብ ቢሆንም የእሱን ሲኔየሮች ከኃላፊነት ገለል በማድረግ እሱ ወደመሪነቱ እንዲመጣ የተፈለገ ይመስላል፡፡ ሌትናት ጀኔራል ዮሃንስ ገብረመስቀል ከጄኔራል ሳሞራ ጋር ጥብቅ ወዳጆች እንደሆኑ ይነገርላቸዋል፡፡ ዮሃንስ ከፍተኛ ሀብት እንዳካበቱ ከሚነገርላቸው ጀኔራሎች መካከል ሲሆን በአሁኑ ጊዜ ደመወዙ በአስራ ሺ የሚቆጠር ዶላር እንደሆነ ይጠቀሳል፡፡ ቢሆንም ግን ሀብታምነቱ አሁን የዚህ ደመወዝ ባለቤት ከመሆኑም የቀደመ ለመሆኑ መረጃዎች ያሳብቃሉ፡፡ (ሌትናት ጀኔራል ዮሐንስ የደህንነቱን ስራ በኃላፊነት የሚዘውረው ጌታቸው አሰፋም ድጋፍ እንዳለው ይጠቀሳል፡፡)

በዚያም አለ በዚህ ግን አሁን ላይ ሳሞራ መለስ በህይት እያለ ከነበረው እቅድ በወጣ መልኩ በኢታማዦር ሹምነቱ መቆየቱ ሀቅ እንደሆነ ይገኛል፤ የጡረታ ጊዜውን ማንም ቆርጦ ማስቀመጥ የተቻለው የለም፡፡ በስብሰባዎች ወቅት በድፍረት እያንዳንዱን ነጥብ እያነሳ ይገስጻቸው ነበር የሚባልለት ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ አሁን የለም፡፡ ስለዚህም አሁን ሳሞራም ሆነ ሌሎች ጄኔራሎች ተቆጭ የሌላቸው እንደሆኑ ነው የሚነገረው፡፡ በትንሹም ቢሆን አቶ በረከት ስምዖን የመለስን ቦታ ተክቶ ለመገሰፅ የሚሞክርበት አጋጣሚ ቢኖርም እንደመለስ ግን አይደነግጡለትም፤ በስልጣናቸውም ላይ ለውጥ የሚያመጣ መስሎ አይሰማቸውም ነው የሚባለው፡፡ በመጨረሻም፣ የጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝን ሚና እዚህ ላይ ማንሳቱ እምብዛም አስፈላጊ አይመስለኝም፡፡ በእርግጥ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ አዛዥ ናቸው፡፡ ያም ቢሆን ግን ጀኔራሎቹ ለሰውዬው እንደቀድሞው አዛዣቸው መለስ ዜናዊ አድርገው የሚመለከቷቸው አይመስለኝም፡፡ እናም አሁን በሰራዊቱ ውስጥ ወሳኙ አድራጊ ፈጣሪው ሰው ሳሞራ የኑስ ለመሆኑ ጥርጥር የለውም፡፡ ለዚያም ይመስላል ከሰራዊቱ ለተነሳለት ጥያቄ ‹‹ካልፈለግህ ልቀቅ…›› ምላሽ ለመስጠት የበቃው፡፡ ለዚያም ይመስላል ለቀጣይ የስልጣን ጊዜው ‹ስጋቴ› ናቸው ያላቸውን ሲኒየር ጀኔራሎችን ከአዛዥነት ያነሳቸው፡፡

ተባበር ወይንስ ተሰባበር!? (ዋስይሁን ተስፋዬ)

$
0
0

ሰኔ 10 ቀን 2006 እ.ኢ.አ.
ከዋስይሁን ተስፋዬ


በኢትዮጵያ ሃገራችን በፍቅር፣ በመተሳሰብና፣ በመቻቻል ለዘመናት የኖረ ህዝብ እርስ በርሱ በጥርጣሬና በጥላቻ ሲጎሻሸም፤ ቤተሰብ ከቤተሰብ መተማመን ጠፍቶ ግለኝነት ሲነግስ፤ የአብሮነታችን ማሰሪያ የሆነው ፍቅራችን ጠፍቶ አንዱ ብሄር በሌላው ብሄር ላይ ጥላቻን ሲዶልት፤ መከባበራችን ረክሶ አንዱ ሃይማኖት ሌላውን ሲጠራጠር፤ ባጠቃላይ በሃገሪቱ ፍቅር ጠፍቶ ጥላቻ ሲነግስ በማየቴ አዘንኩ። ገዢው የኢህአዴግ ከፋፋይ ሥርዓት የዘረጋው አፋኝ መዋቅር ህዝብ ከጥላቻ ውጪ ሌላ ምንም አይነት መረጃ እንዳያገኝ አፍኖ፤ በሃገሪቷ ሰላምና መረጋጋት እንዳይሰፍን፤ ብሎም ኢትዮጵያዊነት ቀስ በቀስ እየተሸረሸረና እየጠፋ እንደሆነ ሳስተውል ደግሞ ፈራሁ። በአንፃሩ ደግሞ ይህ አደገኛ ሁኔታ ለመናገር በሚዘገንን መልኩ አስከፊ በሆነበት በዚህ የጨለማ ዘመን፤ በተቃዋሚስምራሳቸውንሰይመው ‘እኔካልኩትበላይ ምንም ሊሆን አይችልም’በሚልአምባገነናዊአስተሳሰብ፤ በህዝብ ስምለህዝብነፃነትሳይሆን የራሳቸውንየግልፍላጎትለማሳካትየህዝብንበደልበማባባስ ላይ የተሰማሩ ስብስቦች እንደ አሸን በዝተው ስመለከት ተረበሽኩ። በመሆኑም በሃገራችን በጎ ነገር እንዲሰፍን በመመኘት፤ ያላስተዋለ ተገንዝቦ፣ አይቶ ዝም ያለም የሃገርና የህዝብ ውድቀት ነውና ማፈግፈጉን ትቶ ወደ እውነተኛው የህዝብ ነፃነት መንገድ ይራመድ ዘንድ፤  በዚህች አጭር ፅሁፍ ጥቆማዬን ለአንባቢያን ማቅረብን ፈቀድኩ።

ሁላችንም እንደምናውቀው የኢትዮጵያ ህዝብ ደህንነትና የሃገሪቱ ህልውና በኢህአዴግ መንግስት በጎ ፍቃድ ብቻ የሚወሰን መሆኑ ለሁሉም ኢትዮጵያዊ ግልፅ ነው። በመሆኑም መንግስት እንዳሻው ሃላፊነት በጎደለው አካሄድ ህዝብን ለዘመናት ሲያፈናቅል፤ ንጹሃን ዜጎችን መጥፎ ስም በመስጠት ባልሰሩት ሃጥያትና በተፈበረከ የሃሰት ውንጀላ በየእስር ቤቱ እንዲማቅቁ ሲያደረገ፤ የሃገሪቱን መሬት በፈቀደው መልኩ ለባእዳን ሃገራት ሲያድልና ሲሸጥና ብዙ ሌሎች በደሎችን በህዝብና በሃገር ላይ በተደጋጋሚ ሲፈፅም ማየት የተለመደ ሆኗል። በኔ አስተሳሰብ ኢህአዴግ ይህንን ማድረግ የቻለበት ዋንኛው ምክንያት የሚዲያ ተቋማትን ሙሉ ለሙሉ መቆጣጠር በመቻሉ ነው። በሃገራችን የሚገኙት መንግስታዊ የሚዲያ ተቋማት የኢህአዴግን የዘረኝነት ፖሊሲ ብቻ በመስበክ በተለይ ወጣቱ ትውልድ ስለ ሃገሩ አንድነት፣ ስለ ህዝቧ ፍቅርና፣ በሃገሪቱ ስላሉት የተቃዋሚ ድርጅቶች እንቅስቃሴ እንዳይሰማና እንዳያውቅ በማድረግ አስተሳሰቡ ከአካባቢው የማያልፍ ጠባብ አድርጎታል። ለዚህም በቅርቡ በኦሮሚያ ክልል በዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ሲተውኑት ያየነው ትእይንት አይነተኛ ምስክር ነው። ለአንድ ሃገርና ህዝብ የወደፊት አቅጣጫና ህልውናን በመወሰኑ ረገድ ሚዲያ እጅግ ወሳኝ ድርሻ አለው።ኢህአዴግ በሚቆጣጠራቸው የሚዲያ ተቋማት የሚያሰራጨውን የዘረኝነትና የእርስ በርስ የጥላጫ መርዝ በመቋቋም የነፃነት ትግሉን ወደፊት መግፋትና ለውጤት ማብቃት የሚቻለው፤ ኢህአዴግ እየፈፀማቸው የሚገኙትን በደሎች ከማጋለጡ ባሻገር፤  ህዝቡ በተቃራኒው ስለአንድነትና ፍቅር እንዲሁም ስለተቃዋሚዎች በቂ እውቀት እንዲኖረውና፣ ልዩነቶቻቸውን አጥብበው በጋራ እንዲሰሩ የሚገባውን ጫና እንዲያደርግ፣ አልያም የመረጠውን መቀላቀል ይችል ዘንድ ሁለገብ መረጃዎችን በስፋት ለህዝብ ለማድረስ የሚሰራ የሚዲያ ተቋም መገንባት ሲቻል ብቻ እንደሆነ ይሰማኛል። በተለይ እንደ ኢህአዴግ የሚዲያ ጠላት በሆነና ህዝብን በዘር፣ በጎሳ፣ በሃይማኖት፣ ከፋፍሎ የእርስ በርስ ጥላቻና ቂም ለማስፋፋት ታትሮ በሚሰራ አረመኔአዊ አገዛዝ ስር ለወደቀ ህዝብ ነፃ የመረጃ ስርጭት እጅግ አስፈላጊ ነው።  

ሁላችንም እንደምናየው የኢትዮጵያ ህዝብ በአሁኑ ወቅት የተቃዋሚ ቡድኖች ከመጠን በላይ በመብዛታቸው ምክንያትና መረጃ በብቃት ስለማይደርሰው፤ የድርጅቶቹን አላማ፣ ግብ፣ ራእይ፣ በጎ ጎኖችና ግድፈቶች፣ እንዲሁም ሌሎች ልዩነቶቻቸውን በቅጡ መለየት ተስኖት፤ ምኑን ከምኑ፣ የትኛውን ከሌላኛው መለየት ባለመቻሉ ግራ በመጋባቱ ‘የነፃነት ትግል የውሸት፤ ፖለቲካ አይንህ ላፈር’ በሚል የተሳሳተ አስተሳሰብ ተወስኖ፤ የሚደርስበትን ችግር ለማስቆም በጋራ ከመታገል ይልቅ በዝምታ መቀመጥን መርጦ ይገኛል። በመሆኑም የተቃዋሚ ድርጅቶች ያለ ህዝብ ተሳትፎ ብቻቸውን ሲያጨበጭቡ ይታያሉ።   

ከላይ ለመግለጽ የሞከርኳቸውንና ሌሎች መሰል ችግሮችን ለመቅረፍ ዋንኛ መሳሪያው ብቃት ያለው የሚዲያ ተቋም መኖር በመሆኑ የተለያዩ የተቃዋሚ ቡድኖች ተቋማትን መስርተው ሲንቀሳቀሱ እናያለን። ነገር ግን እዚህጋ ሊሰመርበት የሚገባው ጉዳይ ተቋማቱን መመስረት ብቻ ሳይሆን የሚያስተላልፉት የመረጃ ይዘቶችና አይነቶች እጅግ ወሳኝ መሆናቸውን ነው። በኔ እይታ የሚዲያዎች አትኩሮት በተለየ ሁኔታና በስፋት፤ በተቃዋሚዎች መካከል ያሉትን ልዩነቶች፣ የተቃዋሚዎችን በጎ ጎኖችና ግድፈቶች፣ ከገዢው መደብ ጋር ያላቸውን ልዩነቶች በመረጃ ማቅረብ፣  ለሁሉም የፖለቲካ ሃይሎች ያለ አድልዖ እኩል መድረክ የሚሰጡና በሃገሪቷ ታሪካዊ፣ ፖለቲካዊና ማህበራዊ ጉዳዮች ላይ ተቃራኒ አመለካከቶች ያሏቸውን ምሁራንንና የፖለቲካ ሰዎችን በማወያየት ህዝብ በስነልቦና በእውቀት እንዲጎለብት በስፋት የሚሰሩ ሊሆኑ ይገባል። ከዚህ መነሾነት ሲስተዋሉ በአሁኑ ወቅት ለኢትዮጵያ ህዝብ እውነተኛ መረጃን ለማስተላለፍ በሚል አላማ ከሚሰሩት የሚዲያ ተቋማት አብዛኛዎቹ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ የኢህአዴግን መሰረታዊ አላማዎች ከማስተጋባት ያለፈ የሚጨበጥ ስራ ሲያከናውኑ አይታዩም። በእርግጥ አንፃራዊ በሆነ ሁኔታ ስመለከታቸው እንደ Addis Dimts Radio፣ SBS Australia፣ የVOA እሰጥ-አገባና እንወያይ የራዲዮ ዝግጅቶች ሊመሰገኑ  የሚገባ መሆኑን ለመጠቆም እወዳለሁ። 

ከአድማጮችና ከደጋፊዎች ብዛት አንፃር የኢሳት ራዲዮና ቴሌቪዥን ከፍተኛውን ድርሻ የሚይዝ ስለሚመስለኝ ሃሳቤን ለመሰብሰብ ይሆን ዘንድ፤ ታዋቂ ሰዎችና የፖለቲካ መሪዎች ከአድማጮች ለሚቀርቡ ጥያቄዎች በኢሳት ራዲዮ ምላሽ የሚሰጡበት፤ የ “ጥያቄ አለኝ” ዝግጅት ላይ፤ የኢሳት ቴሌቢዥንና ራዲዮ በማኔጅመንት ዳሬክተሩ በአቶ ነአምን ዘለቀና በጋዜጠኛ ብሩክ ይባስ ትብብር መላሽ የነበረበትን ለሁለት ሳምንታት የተላለፈ ዝግጅት ላይ ከአንድ አድማጭ የቀረበ ጥያቄንና ከኢሳት የተሰጡ መልሶችን እንደምሳሌ ማንሳት አስፈላጊ ነውና ከዝግጅቱ ከታዘብኩት ጥቂት ልበል። እኝህ ኢትዮጵያዊ የኢሳት አድማጭ ለኢሳት ያቀረቡት ጥያቄ ከላይ ካነሳሁት መሰረታዊ ሃሳብ ጋር በፅኑ ስለሚገናኝና አድማጩ ኢሳትን ሊያስገነዝቡ የሞከሯቸው ጭብጦች በአምባገነን ስርዓቶች ለአመታት ሲሰቃይ ለኖረው ህዝብ ነፃነት መጎናፀፍ ጉልህ ሚና ስለሚኖራቸው፤ ጥያቄያቸውም የበርካታ ኢትዮጵያውያንም ጥያቄ እንደሆነ ስለምገምት ለአንባቢያን ጥያቄውን አቀርባለሁ።  

ምስጋና ይህን ወሳኝ ጥያቄ ላቀረቡት ለእኝህ ቀና ኢትዮጵያዊ የኢሳት አድማጭ ይድረስና፤ ባይሳካም የጉዳዩን ወሳኝነት ለማሳሰብ አቀራረቡን የበለጠ ግልፅ አድርገው በሁለተኛው ሳምንትም በድጋሚ ጠይቀዉት ነበር።  ወደ ተነሳሁበት ጉዳይ ልመለስና፤  እንደኔ አረዳድ የጥያቄያቸው መንፈስ ይህን ይመስላል፤ “እስካሁን ድረስ የተለያዩ መረጃዎችን ስትሰጡን ኖራችኋል። ነገር ግን የምትሰጡን መረጃዎች የኢትዮጵያ ህዝብን ወደ ድል ሊያበቁ አልቻሉም። ሁላችንም እንደምናየው ወያኔ የሚፈልገዉን ነገር ከማድረግ የሚያግደው ምንም ሃይል ሊፈጠር አልቻለም። የዚህ ዋና ምክንያት ደግሞ የምትሰጡት መረጃ ወያኔ በደሉን ከህዝብ ለመደበቅ የጭቆና ስልቱን በመቀየር ስህተቱን እንዲያርም ከማድረግና ከማገልገል በስተቀር ለህዝብ የረባ ፋይዳ አላስገኘም።  ለወያኔ ደካማ ጎኑን እንደምትነግሩት ሁሉ፤ ለተቃዋሚዎችም ስህተታቸውን እንዲያርሙ እንድታሳስቧቸው ዘንድ፤ ብሎም ተቃዋሚዎች እየሰሩት በሚገኙት በደል ምክንያት ለነፃነቱ ላለመቆም ሳይወድ እንዲሸሽ ለተገደደው የኢትዮጵያ ህዝብ ብርታት እንደሚሆነው በማስገንዘብ ከብዙ አድማጮች አስተያየት ቢሰጣችሁም፤ ተግባራዊ ልታደርጉ አልቻላችሁም። የኢትዮጵያ የተቃዋሚ ሃይሎች ኢህአዴግ ከሚያጠፋው በላይ በኢትዮጵያ ላይ ትልቅ ጥፋት እያደረሱ ይገኛሉ፤ ምክንያቱም እኔ ካልኩት ሃሳብ በላይ ማንም ሊሆን አይችልም ብለው ስለሚያምኑ፤ ልስራ ብሎ የሚመጣውን አንዱ ሲያዳክም፤ አንደኛው ሌላኛውን ሲያጠፋ እያየን እንገኛለን።  ፊትለፊት አምጥታችሁ አገናኝታችሁ በጋራ እንዲሰሩ ልዩነቶቻቸውን ህዝብ አውቆ እንዲፈርድና የመረጠውን እንዲቀላቀል የማትረዱት ለምንድነው?”። 

ለጥያቄው በትብብር የሰጡትን መልስ መሰረት በማድረግ ለአቶ ነአምን ዘለቀና ለጋዜጠኛ ብሩክ ይባስ ማሳሰብ የምፈልጋቸው ነጥቦች፤ የእኚህ  አድማጭ ጥያቄ የሁሉም ኢትዮጵያዊ ጥያከ መሆኑን፣ የተጠየቀው ጥያቄ እርስዎ(አቶ ነአምን) አስረግጠው እንዳስገነዘቡን የኢሳትን ነፃ ሚዲያነት የሚጋፋ ሳይሆን በተቃራኒው ኢሳት እንደ አንድ ለኢትዮጵያ ህዝብ መረጃ ለማቀበል የሚሰራ ነፃ የሚዲያ ተቋም በስፋትና በከፍተኛ ትኩረት ሊሰራበት የሚገባዉን ወሳኝ ጭብጥ የያዘ መሆኑን፣ ለህዝብ ነፃነት የሚበጀው አንድ የተቃዋሚ ድርጅት ትእይንት ባዘጋጀ ቁጥር ብቻ ወይንም ገዢው መንግስት በህዝቡ ላይ በደል በፈጠመ ጊዜ ብቻ የተቃዋሚ መሪዎችኒና ታዋቂ ግለሰቦችን ማነጋገር ሳይሆን፣ የህዝቡን የመረጃ ክፍተት መሰረት ያደረገና ዘላቂነት ያላቸው የተጠኑ ውይይቶችን ለህዝብ ጆሮ ማቅረብ እንዳለበት ለማስገንዘብ የቀረበ መሆኑን አውቃችሁ ግዴታችሁን ለመወጣት ብታተኩሩ መልካም ነው፣ የሚሉ ናቸው።

በዚህ አጋጣሚ የኢሳት ራዲዮና ቴሌቪዥን ገዢው የኢህአዴግ መንግስት በኢትዮጵያ ህዝብ ላይ የሚያደርሳቸውን በደሎች በማስተጋባት ብሶቱን ለማሰማት እለት ተለት የሚያደርገውን ጥረት ለማድነቅ እወዳለሁ። ሆኖም በኔ እይታ ይህ የኢሳት ራዲዮና ቴሌቪዥን ጥረት ብቻውን፤ ለህዝብ ብሶቱን ከማሰማት ያለፈ አስተዋዕፅዎ ይኖረዋል ብዬ አላምንም። በመሆኑም ኢሳት እንደ ነፃ የሚዲያ ተቋም ህዝቡ በቂ መረጃን አግኝቶ እየደረሱበት የሚገኙትን ከመጠን ያለፉ ችግሮች ለማስቆምና፤ ብሎም ለነፃነቱ በጋራ ትግሉን ይቀላቀል ዘንድ ለማስቻል፤ የህዝብ ብሶትን ከማሰማት ባለፈ እጅግ በጣም ብዙ መስራት የሚጠበቅበት መሆኑን በማስገንዘብ፤ የህዝብ ነፃነትን  እውን ለማድረግ በሚደረገው ትግል ላይ እንደ ሚዲያ ሃላፊነቱን ለመወጣት መጠነ ሰፊ የሆነ የዝግጅትና የአቀራረብ ለውጥ ማድረግ እንደሚኖርበት ጥቆማዬን አቀርባለሁ።

ይህን ሃሳብ ሳካፍል ፅሁፌን ያየ ያነበበ የኢትዮጵያ ልጅ ሁሉ፤  እኔ የተረዳሁትን ተረድቶ መፍትሄውን እንዲፈልግ፤ አልያም ሃሳቤን ለማካፈል የሞከርኩት ነፃሚዲያያጎናፀፈኝንእድል’ተጠቅሜ ነውና፤ ከተሳሳትኩ የመታረም መብቴ የተጠበቀ መሆኑን እንዲረዳልኝ እጠይቃለሁ። ስለሆነም የኔ ማጠቃለያ የነፃ ሚዲያዎች ትኩረትና የአንባቢያን ጠቃሚ አስተያየት እንደሚሆን በእጅጉ ተስፋ አደርጋለሁ።

ቸር እንሰንብት

ከዋስይሁን ተስፋዬ

ttwasyhun@gmail.com

Comment

 

የልብ ርትዑ አንደበት! (ሥርጉተ ሥላሴ)

$
0
0

ከሥርጉተ ሥላሴ 17.06.2014 (ሲዊዘርላንድ ዙሪክ)
Haile Medhin Aberaልክ የዛሬ አራት ወር ይህችን ዕለት ነበር ጀግና ካፒቴን አበራ ሀይለመድህን ሲዊዘርላንድ ጄኔባ ላይ ካለምንም እንከን፤ ካለምንም ግድፍት፤ ከለምንም ጥፋት ልቡ የተናገረውን ስኬታማ ክንውን ያደመጥነው።

የልቡ ርትዑ አንደበት መድረኩ ሆነ አድማጩ ድርጊቱ ብቻ እንዲሆን ወስኖ የማድረግ አቅሙን፤ የልቡን ፈቃድና ውሳኔ እንድናይ፤ እንድንማርበት ፈቀደልን። ተባረክ የእኔ ጌታ!

እንሆ የተባ ርትዑ የልብ አንደበት በሙሉ መስናዶ ተደራጅቶ የልብ ካደረስ ልክ ዛሬ አራት ወር ሆነው።

በዚህ በተሸኙ ወራቶች ስሜቱን? ፍላጎቱን? ውስጡን ማዬት ባይቻልም ልቡ የነገረውን፤ ልቡ የወሰነለትን፤ ዘመን የፈቀደለትን ተግባር ከዋኝ በመሆኑ መንፈሱ እረፍት ላይ ይሆናል ብዬ አስባለሁ። ከሁሉ በላይ ደግሞ የአንድም ፍጥረተ – ህይወት አካል ሆነ መንፈስ አደጋ ላይ ሳይጥል፤ ቂም ሳይተክል፤ ደም የሚያጋባ እርግማን ሳይፈጥር በጸጥታና በዝምታ የተከወነ መሆኑ ቁጭ ብሎ ሲያስበው ሆነ ሲመረምረው ሊጸጽተው የሚችል አንዳችም ነገር ከቶ እንደማይኖር ይሰማኛል።

ጀግና አበራ ሀይለመድህን የልቡ አንደበት ጥሩ ተናጋሪ የመሆኑን ያህል ጥሩ አድማጭም መሆኑን በቅደም ተከተል የወሰዳቸው እርምጃዎችና ፍሬዎቹ እራሳቸው መስካሪዎች ናቸው። ትውልዱ ከዘመኑ መቀደም ነገን አስልቶ ጥንቃቄን – በብልህንት፤ ብልህነትን – በማስተዋል፤ ማስተዋልን – በድርጊት ማስጌጥ አብነቱን አንቱ ያሰኘዋል። ዛሬ በዬዩንቨርስቲዎች የሚያልቁት ወጣቶች፤ በገፍ ወደ እስር ቤት የሚጣሉት ቀንበጦች፤ አብሶ ሴቶች ከግፉ በተደራቢነት በእዬስር ቤቱ የሚደርስባቸው ፆታዊ ጥቃቶች እና እንግልቶች ሁሉ ሲሰሉ ወጣት አበራ ሀይለምድህን ዬወሰደው እርምጃ አስፈላጊና የተገባ ወቅታዊ መሆኑን ያመሳጥርልናል።

ዕለታዊ ህይወት ለመምራት በስጋት ታፍኖ ራህብን ማስተናገድ፤ የመኖርን ነፃነት በጠራራ ጸሐይ ተቀምቶ ከሁለተኛ ዜግነት ደራጃ በታች መማቀቅ፤ የሰው ልጅ ለትንፋሹ እንኳን ይለፍ ደጅ ጥናት ወረፋ የሚጠይቀብት ቀን ላይ መደረስ፤ ዜጋ ለሚለብሰው ልብስ ቀለምን እንኳን ተሳቆ መሆኑ ሁሉም ሲጠቃለሉ በተለይ ነገ ኢትዮጵያን የሚረከቡ የብሩህ ራዕይ ባለቤት ወጣቶች „አሻምን“ በተገኘው መንገድ ሁሉ ለመግለጽ ቆርጠው በዬደቂቃው መሰዋታቸው ሲታሰብ ይህ ብርቅ ወጣት የወሰደው እርማጃ ሃቅን ያበራ፣ እውነትን ያነገረ፣ ለእውነት ዘብ አደር የሆነ ስለመሆኑ አስተርጓሚ ፈጽሞ አያስፈልገውም።

ዛሬ ዘመን ባመጣው የቴክኖሎጂና ሳይንስ የመረጃ ፍሰት የኢትዮጵያ ወጣቶች ትውልዳዊ ድርሻቸውን ለመወጣት ሌትና ቀን ሲባትሉ፤ ወያኔ ግን የሳይንስና ቴክኖሎጂ እድገት በመከተር ለእስር የዳረጋቸው ወጣት የብሎገር ትንታጎች፤ የሚረዷቸው ወላጆቻቸውን ሆነ የሚሳደጓቸውን ታናናሾቻቸውን ሜዳ ላይ ካለ ባሊህ ባይ ሲበተኑ ለሚያይ ህሊና በእርግጥም ጀግና አበራ ሀይለመድህን ዬወሰደው እርምጃ የጠራ – እውነትን የተንተራሰ ስለመሆኑ ያለ ይግባኝ ሊያስማማ የሚችል ፍሬ ነገር ሊሆን ይገባል።

ወጣት ጋዜጠኞች ብእራቸውና ጸጋቸው ያዬውን – ያደመጠውን ነው የጻፉት። ከዚህ ውጪ የፈጸሙት አንዳችም በደል የለም። ነገር ግን ከቅርብ ስለተገኙ ብቻ የቋሰኛው ወያኔ የጥቃት ሰለባ ነው የሆኑት። ታስረው በእግር ብረት እንደ ወንጀለኛ መቀጣጫ እንዲሆኑ ሲንገላቱ ቀን እራሱ ደም ያነባል። ምን አደረጉ እነዚህ ንጹኃን? ዘመን የሸለማቸውን ተጋሪ በመሆናቸው እንዴት እንደ ወንጀለኛ በሰንሰለት ይታሠራሉ?!

ስለሆነም ትውልዱ በወል መከራው – በጋራ እንባው፤ በሁለገብ ፍዳው ላይ ቢያንስ መስማማት ያለበት ይመስለኛል። ትውልዱ በተወለደበት በሀገሩ በመገለሉ – በመሬቱ ባይተር መሆኑ – በቀዩ መገፋቱ – በባዕቱ በጥቂቶች በመገላመጡ  እነዚህን ጉልህ ጥቃቶቹ አቅምን ፈጥረው የራዕይን ስምረት ሊያሳኩ የሚችሉ መንገዶችን እንዲጠረጉ መትጋት እንዳለበት ደወሉ ሊሆኑለት ይገባል እላለሁ፤ ካፒቴን አበራ ሀይለመድህን አበራ ያደረገው ይህንን ነው። ያደመጠውን — ያነበበውን —- አመሳጥሮ በተባ ድርጊት ተረጎመው። የልቡ አንደበት ማይክራፎን ወይንም ድምጽ ማጉያ ወይንም መንበር መድረክ አላስፈለገውም – በፍጹም። አጃቢም አላሰኘውም። የፕሮቶኮል ሥነ ምግባር ቅደመ ሁኔታ አልጠዬቀም – በፍጹም። ቁልፍ ከእጁ ነበር – መግል የሚያነባ የግለት ፍዳና ዕንባ። ስለሆነም በማድረግ ብቃት መሪነት „አሻፈረኝን“ ገለጸ።

የልብ ንግግር ህብር ነው። የልብ ንግግር – መስመር ነው። የልብ ንግግር – ደንበር ነው። የልብ ንግግር – የቁስለት ብር አንባር ነው። ዬልብ ንግግር ጥቃት አውጪ – የንቁ መንፈስ ሥር ነው። የልብ ንግግር አጃቢ አልቦሽ – ትጥቀ ሙሉ አሸናፊ ግብር ነው። የልብ ንግግር ለሽ ብሎ በተኛ በጠላት ሰራዊት ላይ ጥቃት ፈጽሞ ገዢ መሬቱን መቆጣጠር የሚያስችል ጉልተ ድል ነው። ረዳት ካፒቴን አበራ ያሰተማረው ምስክር ተግባሩ ይሄውን ነው።

ስለሆነም በተወሰን ደረጃ የእሱ ጉዳይ መልክ የያዙ ሁኔታዎች እንዳሉ ቢደመጡም በዚህ ዙሪያ አቅም ያላቸው ወገኖች ተግተው መሥራት ግን ይኖርባቸዋል። እርግጥ መረጃው እንደ ጠቆመው ፍሬ ነገሩ ትንፋሽን መሰብሰብ ያስችላል። ትንፋሹን በእርግጠኝነት እንዲቀጥል ለማድረግ ግን ጠንካራ ተከታታይነት ያለው ተግባር መሠራት አለበት።  ጊዜያዊ ነገር ጊዜያዊ ቋሚ ደግሞ ቋሚ ነው። ለቋሚ ዕውቅና በርትቶ መትጋት ያስፈልግ ይመስለኛል። ነገ ሌላ ቀን ነው። ሰው ይቀዬራል። ሁኔታም እንዲሁ። ቋሚ ከሆነ ግን መሬት ዬያዘ ይሆናል – እርግጠኝነትንም ያስውባል።

እግዚአብሄር ይመስገን ከሙያ አንፃር ዶር/ ሼክስፔር ፈይሳ ህይወታቸውን የሰጡበት ተግባር ከውነዋል። ጉዳዩ እትብታዊ ባለቤት ከሙያ አንጻር አለው። ይህም ቢሆን ጎን ለጎን እገዛው ፊርማ ማሰባሰቡ ወዘተ ተጠናክሮ መቀጠል አለበት። ዘነፍ ያለች ነገር ቢፈጠር ጥቃቱ ብዙ ነገር ነው የሚያደቀው አምክንዮም እንዲሁ። ብዙ ተስፋን ነው የሚያራቁተው። ብዙ ነፍስ ነው ጥግ አልባ የሚሆነው። ስለሆነም እኔ እላለሁ ማሸነፍን በሁለት እግሩ ማቆም በእጅጉ ያስፈልግ ይመስለኛል። ሀገሩ ሲዊዝ ነውና።

በተረፈ የኢትዮጵያ ወቅታዊ ሁኔታዎች የመወያያ መድረክ በቀጥታ ጉዳዩ ለሚመለከተው የሲዊዝ መንግሥታዊ አካል የጻፈው ደብዳቤ ከልብ የሚገባ ነው። አምላካችን የሰውን ልጅ ሲፈጥር እንዲያመሰግነው ብቻ ነው እንጂ ጌታችን መዳህኒታችን እዬሱስ ክርስቶስ ሁሉም ያለው የሁሉም ጌታ ልዑል ነው። የኢትዮጵያ ወቅታዊ ሁኔታዎች የመወያያ መድረክ በማህጸረ ስሙ ከረንት  ኃላፊነቱን ወስዶ እሳከሁን የሲዊዘርላንድ መንግሥት በረዳት አውሮፕላን አብራሪ አበራ ሀይለመድህን ጥያቄ ዙሪያ ለወሰዳቸው በጎ ምላሻዊ  ተግባራት እንዲሁም ቀጣይ እንክብካቤም ሁኔታውን ዘርዝሮ ምስጋና መጻፉ የላቀ ሥልጡን ተግባር ነው። ብልህነትም – መብልጥም፤ እንዲሁም ማስተዋልም ነው። ይህ በኸረ ተግባር ቀላል ሊመስል ይችል ይሆናል። እንደ እኔ በጥቂቱ ስሜቴ እንዲህ ነው ያዬው —-

  1. የጉዳዩ ባለቤትነትን አመሳጥሯል፤ አለሁ ባይነት ሲታደሉት ብቻ የሚገኝ ምርቃት – እናትነት!
  2. መስዋዕትንት ለመቅደም ፈቅዷል፤ በከፋ ቀን መገኘት – ማተበኝነት – ኪዳንም፤
  3. የጀግናውን ችግር ፈቅዶ በይፋ ተጋርቷል፤ አካላዊነትን በመሆን አቅልሟል።
  4. ከሁሉም በላይ ኢትዮጵያዊ ጨዋነትን አብራርቷል፤ የታሪካዊት ሀገርን የኢትዮጵያ ክብር ጠብቋል። አደራ አውጪነት!
  5. የመንፈስ ሥልጡን ህዝብ አምከንዮ በሚገባ ገልጧል፤ የራቀ የበለጠ አቅምን ማሳዬት ግልጽነት በብልህነት።
  6. የወገኖቹን ወላዊ የዕንባ አጋርነት ተስፋነትን አመሳክሯል፤ ብቻውን አለመሆኑን በቅኔ – ቃኝቷል።
  7. የጉዳዩ ተከታታይ ሂደትን – ወገኖቹ በንቃት መታደማቸውን  አሳምሮ ተርጉሟል፤
  8. ለነገን ቀና መንገድን ጠርጓል – ድልዳል አበጅቶለታል ለቀጣይ ፍላጎቱ — በትህትና።
  9. ለፈጣሪ አምላክም ተመችቷል። „ተመስገን!“ ማለት መምህር ነውና። „እናመሰግናለንም“ ትህትና በአክብሮት ነው።

http://ecadforum.com/2014/06/06/switzerland-thank-you-for-granted-resident-status-to-ethiopian-airlines-co-pilot/ ከረንት እኮ ከምሥረታው ጀምሮ እኔ ነኝ ያለ የፖለቲካ ድርጅት ባለነሰ እጅግ የላቀውን  ትውልዳዊ ሃላፊነት የከወነ የመወያያ መድረክ ነው። ሀገራዊ ጉዳዮች መሬት ይዘው በሁለት እግራቸው እንዲቆሙ –  መንፈስን በማደራጀት፤ ከግለሰብ ህይወት ጀምሮ እስከ ግዙፉ የፖለቲካ ተግባራዊ እንቅስቃሴ ድረስ በመሆን ሸማ የከበረ ነው። መሬት የያዘ ጉልበታማ ሁለገብ  ክንውን ያበራ የመወያያ መድረክ ነው። የከረንት አንድ ሰው ባለበት ቦታ – አንድ እራሱ ግን እንደ አስር ነው። ከከረንት በፈለገው መልክና ሁኔታ አባልተኛው ቢለቅ እንኳን የከረንት ቤተኝነት ስሜትን ሆነ ንጹህ ፍቅር እኔ ነኝ ያለ ጀግና መፋቅ ከቶውንም አይችልም – ከረንት ባዕት ነው እንደዚህ ልበለው። እኔም የከረንት – ከረንትም የእኔ። እንደዚህ ባሉ ባለቤት ባጡ ጉዳዮች ደግሞ ከረንት እንዲህ የግንባር ሥጋ መሆኑ እጅግ ያስመሰግነዋል። የእኔም ብትሆኑ እግዚአብሄር ይባርካችሁ።

እርገት ይሁን — ልብ ያዘዘውን – ልብ የተለመውን – ልብ ያቀደውን – ልብ የቆረጠበትን – ልብ የወሰነለትን – ልብ የቆረበበትን የምልእተ ድምጽ ግፍ አድማጭ ሰው እራሱ ልብ ነው! አዎን! ጀግና አበራ ሀይለምድህን ልብም – የልብ -ልብም – ልባምም ነው። ሙያን በልብ የሞሸረ ጽናታዊ ዓዕማድ!

የኔዎቹ የፊታችን ሃሙስ በተለመደው ሰአት ከ15 እስከ 16 Radio Tsegaye  Aktuell Sendung www.tsegaye.ethio.info  አብረን ናፍቆትን እንታደም። ስለሆነም የቻላችሁ አዬር ላይ ያልቻላችሁ በማግስቱ ሲለጥፉት ከቻላችሁ አዳምጡ – በትህትና። በተረፈ ይህቺን ቀነ 17.06.2014 የጀግናን ፎቶ መንበር ላይ ማደረጉን አትዘንጉ እሺ! ሺዎችን ማፍራት የሚቻለው ከእጅ የገባን ድንቅ ማክበር ሲቻል ብቻ ነው …. ቸር ያሰማን –  ቸር እንሁን። አሜን!

 

ፈተናን ከመፈጠሩ በፊት አሸንፎ የተፈጠረ ሚስጥር – ኢትዮጵያዊነት!

ልብ ያለው ጀግና የልቡን የሚያደርስልት እሱ እራሱ ብቻ ነው!

 

እግዚአብሄር ይስጥልኝ።

« ፀሎታችን በቤታችን » የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ እምነት ተከታዮች የፀሎት ቦታ እና የመቃብር ስፍራ ጥያቄ በሳውዲ አረቢያ ።

$
0
0

Ethiopian Hagere ጀዳ በዋዲ

« ፀሎታችን በቤታችን »   የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ እምነት ተከታዮች የፀሎት ቦታ እና የመቃብር ስፍራ ጥያቄ  በሳውዲ አረቢያ ።

በተለያዩ ግዜያት   ህጋዊ እና ህገወጥ በሆነ መንገድ ተሰደው ወደ ሳውዲ አረቢያ ከሚገቡ ኢትዮጵያውያን መሃከል ጥቂት የማይባሉ  የኦርቶዶክ እምነት ተከታይ ወገኖቻችን የህዝብ ሙስሊሙን ሃይማኖታዊ ደንብ እና ስረአት   አክበረው እንደሚኖሩ ይታወቃል ። እነዚህ  በሃገሪቱ  ግዛቶች ሪያድ ጅዳ ደማም እና ጅዛን በሚባል ክፍለ ግዛቶች ውስጥ በተለያዩ ስራዎች ላይ  ተሰማርተው  እንደሚኖሩ የሚነገረው  የእመንቱ ተከታዮች በደስታም ሆነ በሃዘን ግዜ ሃይማኖታቸው  የሚያዘውን የፀሎት ስረአት ሃይማኖታዊ ወግ እና ስረአት  ጠብቀው ለፈጣሪያቸው ጸሎት ማድረስ እንደማይቸሉ የሚገልጹ ምንጮች ሳውዲ አረቢያ በስላማዊ ህግ የምትመራ  የእስልምና ሃይማኖት ተከታይ  እንደመሆኗ መጠን  ሌሎች ሃይማኖቶችን ማራመድ በጥብቅ የተከለከለ በመሆኑ በመንግስት ዘንድ በይፋ ከሚታውቀው ሃይማኖት ውጭ  ምንም አይነት አማራጭ የጸሎት ስፍራዎች ባለመኖራቸው  በኢትዮጵያውያኑ የኦርቶዶክስ እምነት ተከታይ ወገኖቻችን ላይ ከፈተኛ መንፈሳዊ ተጸዕኖ እንዳሳደረባቸው ይናገራል።

comnity jeddእንደ ኢትዮጵያውያኑ በሳውዲ አረቢያ የሌላ እምነት ተከታይ ወገኖች እንዳሉ የሚጠቅሱ ምንጮች  እንደ ፊሊፒንስ ፡ ኔፓል ህንድ ወዘተ  የክርስትና  እምነት ተከታይ እና ሌሎች መንፈሳዊ እምናተ ተከታይ  የውጭ ሃገር ዜጎች በኤንባሲያዎቻቸው  በኩል በሚደረግላቸው ሁለንተናዊ ትብብር እና ድጋፍ ህይወቱ ያለፈች ዜጋን አስክሬን  ተባብረው ለሃሀገሩ አፈር ሲያበቁ ከፈጣሪው ተማጽኖ የራቀውን ፈሪሃ እግዝብሄር  በየሃገሮቻቸው ኮሚኒቲ ተቋማት  ሰር ተሰባስቦ በሳምንት አንዴ « ከፈጣሪው ጋር ተገናኝቶ » ፀሎት የሚያደርስበት   ስፍራ እንደተዘጋጀለት የሚገልጹ እንዚህ ወገኖች  በሪያድ እና በጅዳ የሚገኙ የመንግስት ተወካዮቻችን  ለዜጎቻቸው ደህነት የሚጨነቁ ከሆነ  በጅዳ ቆንስላ ጽ/ቤት በጂዛን የኮሚኒቲ ግቢ እና በሪያድ የኢትዮጵያ የኮሚኒት ካፍቴሪያ አዳራሾች ለዚህ የተቀደሰ ተግባር የሚውል ቤቶቻቸው የማይለየው ግቢውስጥ ያለምንም ቅድመ ሁኔታ የፀሎት ቦታ ሊፈቀድላቸው እንደሚገባ  ይናገራሉ  ።

በየአመቱ በኢትዮጵያውያን የኦርቶዶክስ ም ዕመናን ዘንድ የሚከበሩ በአላትን ከሳውዲ አረቢያ ህግ አንጻር አንድ ቦታ ተሰባስቦ ማክበር እንኳን  እንደማይችሉ የሚናገሩ እነዚህ ወገኖች  ኤምባሲውን በበላይ ነት የሚቆጣጠሩት ዲፕሎማቶች አብዛኛዎቹ የእልምና ሃይማኖት ተከታዮች በመሆናቸው  ዲፕሎማቱ  ለኢትዮጵያውያኑ የኦርቶዶክስ እምነት ተከታይ ትኩረት እንደማይሰጦቸው ይገልጻሉ። ይህ በዚህ እንዳለ ሳውዲ አረቢያ ውስጥ የኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮች መካነ መቃበር ባለመኖሩ በተለያየ ምክንያት ህይወታቸ የሚያጡ የዕምነቱ ተከታዮች እስከሬኖቻቸውን ወደ ሃገር ለመላክ አቅም ስለማይፈቀድ በዲፕሎማቱ ፊርማ እና ሃላፊነት ሆስፒታል «ተላጃ »ገብቷል እየተባለ  ሃይማኖታዊ ስረአትን ባልጠበቀ ምንገድ በአቦጀዴ እይተጠቀለለ ወደ አልታውቀ ስፍራ እንደሚወሰድ ምንጮች አክለው ይገልጻሉ።

ቀደም ሲል አንዲት በቤት ሰራተኝነት ተቀጥራ ትሰራ የነበረች የኦርቶዶክስ እምነት ተከታይ ኢትዮጵያዊት በሪያድ የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ  ግቢ በሚገኝ ግዜያዊ መጠለያ ውስጥ ታማ ያለህክምና እርዳታ ስትሰቃይ ከርማ  ህይወቷ በማለፉ በዲፕሎማቱ ት ዕዛዝ በሳውዲ ማዘጋጃ ቤት ሰራተኞች አስከሬኗ የት እንደደርሰ እንደማይታወቅ የሚናገሩ የልጅቷ የቀርብ ቤተሰቦች  እናት  የልጃቸውን  ሞት ሳይረዱ  ሳውዲ አረቢያ ለስራ የሄደቸው ልጄ ከዕለታት አንድቀን ጥሪት ቋጥራ ትመጣልኛለች  በሚል ተስፋ  የ ልጃቸው ሬሳ  በወግ በመአረግ  ለአፈር መብቃቱን ሳይረዱ መቅረታቸውን በሃዘን የሚገልጹ  ምንጮች በተመሳሳይ መልኩ ህይወታቸው አልፎ መርዶ ነጋሪ ያጡ ኢትዮጵያውያን ወላጆች  ብዛት ቤት ይቁጠረው ብለዋል ።  ፀሎታችን በቤታችን በሚል መሪ ቃል ከእንግዲህ የኢትዮጵያ ኤምባሲ ከጎናችን ሊቆም ይገባል የሚሉ   በሳውዲ አረቢያ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን  የኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮች እስካሁን ሳውዲ አረቢያ ምድር ላይ ህይወታቸው አልፎ  የቀብር ስረአታቸው በወጉ ሳይፈፀም የቀሩ ወገኖችን ሰም ዝርዝር   ዲፕሎማቱ ለቤተሰቦቻቸው በውጭ ጉዳይ ሚንስቴር መ/ቤት በኩል ይፋ ማድረግ እንደሚገባቸው ገልጸው  ወድፊት እንደዚህ አይነቱ አሳዛኝ ታሪክ በዜጎቻችን ላይ እንዳይደገም   ኤምባሲው ከማህበረሰቡ ጋር በመተባበር የጋራ መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ በአሰቸኳይ እንዲቋቋም ጠይቀዋል ። 

riyad ethioian comintyይህ በዚህ እንዳለ ቀደም ሲል ጅዳ ከተማ  እንድ የገል መኖሪያ ቤት ውስጥ ተሰባስበው በጋራ  ፀሎት ሲያደርሱ በነበሩ የኦርቶዶክ ተዋህዶ እምነት ተከታዮች  ላይ የሳውዲ ፀጥታ ሃይሎች  በወሰዱት እርምጃ ከ39 በላይ ኢትዮጵያውያን ለእስር መዳረጋቸው አይዘነጋም  ። ይህንን እምርምጃ የሚያስታወሱ በሳውዲ አረቢያ የሚገኙ የእመነቱ ተከታዮች  የኢትዮጵያ መንግስት ዲፕሎማቶች በአመታዊ በአላትም ሆነ በሳምንት አንዴ ም ዕመናኑ ተስባስበው በጋር መንፈሳዊ ፀሎታቸውን ያለምንም ስጋት የምናደርሱበትንም ሆነ  የእምነቱን ተከታዮች  ሃይማኖታዊ ግንዛቤ እንዲዳበር የሚያስተምሩበት  መንፈሳዊ ማዕከል በኤምባሲው ስር ከሚገኙ ተቋማት ውስጥ ጅዳ ፤ ሪያድ ፤ እና ጂዛን ከተሞች   እንዲፈቀድላቸው ተማጽነዋል ። ለህዝበ ክርስቲያኑ ምዕመናን ጥያቄ መስካት በሳውዲ አረቢያ የሚኖሩ ሙስሊም ኢትዮጵያውያን ከጎናቸው እንደሚቆሙ ከኢትዮጵያን ሃገሬ ምንጮች ማረጋገጥ ተችሏል።   ይህን ጉዳይ በተመለከተ  በጅዳ የኢትዮጵያ ቆንስላ የሁኑትን አቶ ሸሪፍ ኬሬ +96626653444 እና ተቀማጭነታቸው ሪያድ የሆኑትን የኢትዮጵያ አምባሳደር ዶ/ር መሃመድ ሃሰን በዚህ ዙሪያ ለመነጋገር ያደርኩት ሙከራ በተለያዩ ምክንያቶች እስካሁን አልተሳካም ። 

Ethiopian Hagere ጀዳ በዋዲ

ኮካ ኮላ የተባለው መጠጥ አጠገቤ አይደርስም! (ፕ/ር አለማየሁ ገብረማርያም)

$
0
0

ከፕሮፌሰር አለማየሁ ገብረማርያም
ትርጉም በነጻነት ለሀገሬ

ኮካ ኮላ ትክክለኛ ነገር አይደለም!

boycottcocacola1-300x293የኮካኮላ ኩባንያ በታዋቂው የኢትዮጵያ ኮከብ ድምጻዊ ሙዚቀኛ በሆነው በቴዎድሮስ ካሳሁን (ቴዲ አፍሮ) ላይ ያደረገውን ስነምግባርን የጣሰ፣ የዘፈቀደ እና ፍትሀዊ ያልሆነ ድርጊት በማስመልከት የኢትዮጵያ ዲያስፖራ ማህበረሰብ በማህበራዊ እና በመገናኛ ድረ ገጾች ተቃውሞውን በመግለጽ የኮካ ኮላ ምርት እንዳይጠጣ ጥሪውን በማስተላለፍ ላይ ይገኛል፡፡ የዲያስፖፈራው ማህበረሰብ በማያያዝም የኮካ ኮላ ኩባንያ ተንኮልን ባዘለ መልኩ ቴዲን ነጥሎ በማውጣት የአድልኦ ሰለባ እንዲሆን አድርጓበታል በማለት ላይ ነው፡፡ የኮካ ኮላ ኩባንያ 32 የልዩ ልዩ አገሮች ሙዚቃ የቡድን አቀንቃኞችን ለብራዚል የዓለም እግር ኳስ ፌዴሬሽን/FIFA ዋንጫ የመክፈቻ ስነስርዓት ማድመቂያ ሙዚቃ አንድያቀነባበሩ አድርጎ ነበር፡፡ የኮካ ኮላ ኩባንያ በቴዲ አፍሮ ከተቀነባበረው የኢትዮጵያ ሙዚቃ በስተቀር የሁሉንም ዓይነት መሰል ሙዚቃዎች ለቅቋል!

አሁን የኮካ ኮላ ምርት እንዳይጠጣ የሚለውን መርህ እቀላቀላለሁ፡፡ ባለፉት ስምንት ዓመታት ሳቀርባቸው የነበሩትን ትችቶቸን ስትከታተሉ ለቆያችሁ በሚሊዮኖች ለምትቆጠሩ አንባቢዎቸ አሁን የኮካ ኮላ ምርት እንዳይጠጣ የሚለውን ቡድን እንድትቀላቀሉልኝ በአክብሮት እጠይቃለሁ፡፡

የኮካ ኮላ ኩባንያ እና ተወካዮች በቴዲ ላይ ስህተት የፈጸሙ መሆናቸውን ከጥርጣሬ በላይ ተገንዝቢያለሁ፡፡ ስሙን አጥፍተዋል፣ ስብእናውን ዝቅ አድርገዋል እናም በአደባባይ በህዝብ ፊት አዋርደውታል፡፡ ይዞት የቆየውን ዝና እና ክብር ነፍገዋል፣ ስሙን ጥላሸት ቀብተዋል፣ እናም በስራው እና በጥሩ ስነምግበሩ ተጎናጽፎት የቆየውን ጥሩ ስሙን አጉድፈዋል፡፡ ፍትሀዊ ያልሆነ፣ ጨካኝነት የተሞላበት እና የሞራል ስብዕናን ባልተላበሰ ሁኔታ አስተናግደውታል፡፡

እ.ኤ.አ ጁን 7/2014 የኮካ ኮላ ኩባንያ ተወካይ የሆኑ ባለስልጣን የተናገሩትን ዘገባ በመጥቀስ እንደሚከተለው ቀርቧል፣ “ለፊፋ የዓለም እግር ኳስ ዋንጫ ‘ዓለም የእኛ ናት‘ የሚለውን የኢትዮጵያ ልዩ ሙዚቃ ለማቅረብ ዓላማ በማድረግ ዜማውን እንዲያቀርብ እና እንዲቀረጽ እዚህ እኛ የኮካ እስቱዲዮ ድረስ ወደ አፍሪካ እንዲመጣ ተደርጎ ነበር፡፡ ከቴዲ አፍሮ ጋር የተደረገው የኮንትራት ስምምነት ‘ማንዳላ የተወሰነ’ በተባለ መቀመጫውን በናይሮቢ ያደረገ በሌላ ሶስተኛ አምራች ወገን የተፈጸመ ሲሆን ቴዲ አፍሮም ላደረገው ጥረት ሙሉ ክፍያ ተሰጥቶታል፡፡“ የባለስልጣኑ መግለጫ በመቀጠልም እንዲህ ይላል፣ “የድምጽ ቀረጻው ከተጠናቀቀ በኋላ ኮካ ኮላ ሴዋ የተባለ ኩባንያ የሚያዝዝበት የግል መጠቀሚያ ንብረት ነው፣ ሆኖም ግን ሙዚቃው እስከ አሁን ድረስ አልተለቀቀም፣ እናም በአሁኑ ጊዜም እንኳ ሙዚቃው ይለቀቃል የሚል ዕቅድ የለም፡“ በማለት አስተያየታቸውን ቋጭተዋል፡፡

እ.ኤ.አ ጁን 10/2014 በተሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ የቴዲ አፍሮ ተወካይ ባለስልጣን የኮካ ኮላን አስደንጋጭ አዋጅ በማወጅ እና ቴዲ አፍሮ ሙያዊ ያልሆነ ባህሪ አሳይቷል በማለት በኮንትራት ስምምነቱ በግልጽ በተቀመጠው አንቀጽ መሰረት እምነትን የሚያጎድል ድርጊት ሲፈጸም ለህዝብ እንዳይለቀቅ የሚከለክል እንደሆነ አሳውቀዋል፡፡ መግለጫው በማያያዝም የኢትዮጵያን የዓለም ዋንጫ ልዩ ሙዚቃ ላይ ኮካ ኮላ ያልተገደበ ክልከላ ያደረገበትን ምክንያት ለማወቅ እኛ ጉዳዩን በድረ ገጽ ይፋ ከማድረጋችን በፊት ለእነርሱ ብናቀርበውም እስከ አሁን ድረስ ምንም ዓይነት ምላሽ ያለመስጠቱ እንቆቅልሽ ግራ እንዳጋባው ገልጿል፡፡ በዚህም መሰረት የኮካ ኮላ ኩባንያ መጥፎ እምነትን በማራመድ፣ እና “የእራሱን የኮኩባንያ የጽናት፣ የታማዕኒነት፣የህዝብ እምነት እና በእራስ የመተማመን መርሆዎች” በይፋ በመደፍጠጥ “በኩባንያ እብሪት” ተዘፍቆ ይገኛል በማለት ክስ አቅርቦበታል፡፡ የኮካ ኮላ ኩባንያ “የሚያዋርድ፣ የአድናቂዎቻችንን ስሜት እና የኮካ ኮላን ደንበኞች የሚጎዳ መግለጫ በመስጠቱ የተሰማውን ሀዘን ገልጿል፡፡

የቴዲ አፍሮ ተወካይ የኮካ ኮላን ፍረጃ ሙሉ በሙሉ እንዲህ በማለት ውድቅ አድርጎታል፣ “ከቴዲ አፍሮ ጋር የተፈጸመው የኮንትራት ስምምነት ማንዳላ የተወሰነ/Manadala Limited በተባለው በናይሮቢ የሚገኝ የምርት ተቋም ሶስተኛ ወገንተኝነት አማካይነት ነው፡፡“ አቶ ምስክር ሙሉጌታ [የኢትዮጵያ እና የኤርትራ እንዲሁም የማናዳላ ቲቪ ብራንድ ማናጀር] የተባሉ የኮካ ኮላ ተወካይ ባለስልጣን እኛን ከቀረቡን በኋላ ተነሳሽነቱን በመውሰድ የኮካ ፕሮጀክትን ምርጫ እና በቀጣይነትም እኛን ወደ ኮካ ስቱዲዮ በማምጣት የኮካኮላ ማዕከላዊ፣ የምስራቅ እና የምዕራብ አፍሪካ ኃላፊነቱ የተወሰነ ኩባንያ ከማንዳላ ቲቪ ጋር የኮንትራት ስምምነት እንድንዋዋል አድርገዋል…” አቶ ምስክር እንደ ሰራተኛ እና ማንዳላ ቲቪ ደግሞ እንደ በርካታ የሙዚቃ ንብረት አገልግሎቶች ኃላፊ ለኮካ ኮላ ማዕከላዊ፣ የምስራቅ እና ምዕራብ አፍሪካ ተወካይ በመሆን በአንድ ዓይነት የህግ ማዕቀፍ እና በኮካ ኮላ ኩባንያ ላይ ለሚያስከትለው እንደምታ ዋና መስሪያ ቤቱን በአትላንታ ያደረገውን ተቋም በመወከል የተደረገ የኮንትራት ስምምነት ነው፡፡”

እንደዚሁም ደግሞ በኮካ ኮላ መግለጫ ላይ ጉልህ የሆኑ መጣረሶች የተስተዋሉ መሆናቸውን ጠቁመዋል፡፡ የኮካ ኮላ ኩባንያ ከቴዲ አፍሮ ጋር ምንም ዓይነት የኮንትራት ስምምነት ግንኙነት ባይኖረው ኖሮ በእርሱ ላይ ያነጣጠረ ጋዜጣዊ መግለጫ ለመስጠት ለምን አስፈለገው? በሌላም በኩል ኮካ ኮላ ቴዲ አፍሮ “ላደረገው ጥረት ሙሉ ክፍያ ተፈጽሞለታል” ብሏል፣ እንዲሁም የኮካ ኮላ ኩባንያ ከቴዲ አፍሮ ጋር የዓለም እግር ኳስ ዋንጫ ማድመቂያ ሙዚቃን ለማሰቀረጽ የኮንትራት ስምምነት ባይኖረው ኖሮ “የተቀረጸው ሙዚቃ የኮካ ኮላ ሴዋ/Coc-Cola CEWA ንብረት ነው ማለት ለምን አስፈለገው?”

ኮካኮላን የዓለም እግር ኳስ የዋንጫ ጨዋታ ማድመቂያ የሆነውን ልዩ የኢትዮጵያን ሙዚቃ በይፋ እንዳይለቅቀው ያስገደደው ተቃውሞ ምንድን ነው?

ለዓለም የእግር ኳስ የዋንጫ ጨዋታ ማድመቂያ በወጣው የቴዲ አፍሮ ሙዚቃ ግጥም እና ቅላጼ ላይ ምንም ዓይነት የፖለቲካም ወይም ሌላ አወዛጋቢ ጉዳይ የለበትም፡፡ በእርግጥ ቴዲ ኮካ ኮላ ዴቪድ ኮሬይ አንዲገጥም ባደረገው ግጥሞች ውስጥ ቃላትን በቀጥታ ወስዶ “ዓለም የእኛ ናት” በሚል ርዕስ ወደ አማርኛ ተርጉሞ ነበር ያቀርበው፡፡ ሌላ የጨመረውም ሆነ የቀነሰው ነገር የለም፡፡

ቴዲ አፍሮ ከ32 የዓለም የሙዚቃ ጥበብ ባለሙያዎች ለምንድን ነው እንዲነጠል የተደረገው እና የኮካ ኮላ የማዋረድ እና የዘለፋ ኢላማ እንዲሆን የተዳረገው? ኮካ ኮላ ለምንድን ነው የኢትዮጵያን ልዩ የቴዲ ሙዚቃ በአደባባይ ለመልቀቅ ያገደበትን ምክንያት? ለቴዲ ለግሉ ለመገለጽ ፈቃደኛ ያልሆነውስ? ኮካ ኮላ ለምንድን ነው ጉዳዩን ግልጽ በማድረግ በሚሊዮኖች ለሚቆጠሩት የቴዲ አድናቂዎች የኢትዮጵያ ልዩ ሙዚቃ እንዳይወጣ የተደረገበትን ምክንያት ለመናገር ያልፈለገው?

ኮካኮላን ለምን እደምማስወግደው፣

የኮካ ኮላ የዓለም እግር ኳስ ዋንጫ የኢትዮጵያን ልዩ ሙዚቃ ላለመልቀቅ ያወጣው ይፋ የተቃውሞ መግለጫ ለቴዲ አፍሮ ጠላቶች የደስታ እና የደረት ድለቃ ምንጭ ሆኗል፡፡ በድል አድራጊነት እንዲህ በማለት ድሰታቸውን ገልጸዋል፣ “ኮካ ኮላ ቴዲን አሽቀንጥሮ ጣለው!“

ኢንዱስትሪዎች መርዛማ ኬሚካሎችን ወደ ቆሻሻ መጣያ ቦታ እደሚጥሉ ሁሉ እኔም እንደዚሁ ኮካ ኮላን ወደ መርዛማ የኬሚካሎች ቆሻሻ መጣያ ቦታ ጥየዋለሁ፡፡ ይህንን ተመሳስሎ አነጋገር በቀላሉ የምጠቀምበት አይደለም፡፡ “የኮካ ኮላ ኩባንያ ካንሰር አምጭ በሆኑት ፋንታ ፒንአፕል እና ቫውልት ዜሮ ቤንዚን (በሁለት ምርቶቹ ላይ) ያለውን መጠጦች በህግ ተከሶ በስምምነት ጉዳይዩን እልባት ሰጥቷል፡፡“ ኮካ ኮላ 114 የምርት ዓይነቶችን በእንግሊዝኛ ቋንቋ አኳፑሬ ከሚለው ጀምሮ ዚኮ እስከሚለው ድረስ ድረ ገጹ ላይ ይፋ አድርጓል፡፡

አሁን 114 ምርቶቹን ላለመጠቀም የማይለወጥ ዉሳኔ አድርጌአለሁ፡፡ አኳፑሬን፣ ባርቅን፣ ኮካ ኮላን፣ ዳሳኒን፣ ኢቪያንን፣ ፉዝን፣ ጋላሴኡን፣ ቪታሚን ዋተርን፣ ሐይ-ሲንን፣ ኢንካኮላን፣ ጀሪኮንን፣ ኪንሌይንን፣ ሊፍትን፣ ሚኑት ሜይድን፣ ኖርዘርን ኔክን፣ ኦዱዋላን፣ ፓዎሬድን፣ ሬድ ፍላሽን፣ ስፕራይትን፣ ታብን፣ ቫውልትን፣ ወርክስ ኢነርጅን፣ ዚኮን… አነዚህን መጠጦች በምንም ዓይነት ሁኔታ አልገዛም ወይም በምንም ዓይነት መንገድ አልጠቀምም፡፡ ማንም ቢሆን እነዚህን ምርቶች እንዲገዛ ወይም እንዲጠቀም አላደፋፍርም ወይም ደግሞ ሀሳብ አላቀርብም፡፡ በዚህም እውነታ መሰረት በዓለም ላይ የሚገኙ በሚሊዮን የሚቆጠሩ አንባቢዎቼ እነዚህን ምርቶች እንዳይገዙ ወይም ደግሞ እንዳይጠቀሙ በአክብሮት እጠይቃለሁ!

ሁላችንም አንድ በመሆን እንተባበር እና ኮካ ኮላን እና 114 የሚሆኑ ምርቶቹን ባለመጠቀም ከገበያ ውጭ እናድርጋቸው፡፡

ለአስርት ዓመታት የኮ ካላ ኩባንያ ምርቶቹን በደስታ እና የደስታ ስሜት በተቀላቀለበት ዓይነት ሁኔታ እና መፈክሮችን ሊረሱ በማይችሉ ቃላት በማሽሞንሞን የኮርፖሬት ንግዱን ሲካሄድ ቆይቷል፣ ዓለም አቀፋዊ ተቀባይነት እና አጠቃላይ የንግድ እሴቶቹን ሲያስተዋውቅ ቆይቷል፡፡ ባለም የተሰራጩት መፈክሮቹ እንዲህ ይላሉ፣ “ኮካ፡ እውነተኛ ነገር ነው“፣ “ከኮካ ጋር ነገሮቸ ሁሉ የተሻሉ ይሆናሉ“፣ “በአሁኑ ጊዜ ዓለም የሚፈልገው ኮካን ነው”፣ “ኮካ ይህ ነው“፡፡ ኮካ ኮላ እንዲህ ብሎ የሚጀምር የቴሌቪዥን የንግድ ሙዚቃ አለው፣ “የተሟላ ደስታ ባለበት ሁኔታ በመዘመር ዓለምን ለማስተማር እወዳለሁ“፣

ኮካ እንደ እስፕራይት እውነት ሳይሆን ዉሸት
በኢትዮጵያ ነገሮች ኮካ መራራ ያደርጋል፣
ኮካ ኮላ በኢትዮጵያ ጥላቻ እንጅ በኢትዮጵያ ፍቅርን የሚያመጣ አይደለም፣
ኮካ በኢትዮጵያ ህዝብ ላይ እድሜ ሳይሆን ጥላቻ ነው የጨመረው፣
ኮካ ኢትዮጵያውያንን ፈገግ የሚያደርግ ሳይሆን በጥላቻ እንዲሞሉ ያደረገ ነው፣
ብዙ የስኳርነት ባህሪው ስለሚያፍነኝ ኮካን አልጠጣም፣
የዓለም ህዝብ ኮካን ወይም ደግሞ ማንኛውንም 113ቱን የኮካ ምርቶች እንዳይገዛ እፈልጋለሁ፣
በአሁኑ ጊዜ የመጨረሻው እና የዓለም ህዝብ የማይፈልገው ነገር ቢኖር ኮካ ነው፣
ኮካ ዘበት ነው!

የኢትዮጵያ ታዋቂ ሙዚቃ በኩሩው የኢትዮጵያ ወፍ ሲዘመር እንዳይሰማ የተደረገበት ምክንያት ለምን እንደሆነ አውቃለሁ፣

ቴዲ አፍሮ የእራሱን ህዝብ እና አገር ይወዳል፣ ለዚህ ዓላማው አየተቀጣ ይገኛል፡፡

ውርደት ቀለቡ የሆነው እና የትንሽ ጭንቅላት ባለቤት የሆነው በኢትዮጵያ ህዝቦች ጫንቃ ላይ ከፍላጎታቸው ውጭ ተቆናጥጦ የሚገኘው ገዥው አካል ኮካ ኮላ የቴዲን ሙዚቃ እንዳይለቅቀው ተጽዕኖ ያደረገበት ለመሆኑ ምንም ዓይነት ጥርጣሬ የለኝም፡፡ ምክንያቱ ግልጽ ነው፡፡ እነዚህ በበቀል እና በጥላቻ የተሞሉት ገዥ ጽንፈኛ የወሮበላ ስብስብ ቡድን የቴዲ አፍሮ ትክክለኛ ጌታው ማን እንደሆነ ለማሳየት ያደረጉት ከንቱ ምግባር ነው፡፡ እነዚህ የበቀል እና የጥላቻ ቋቶች እንዴት ባለ የማታል ዘዴ እና የተለሳለሰ በሚመስል ማደናገሪያ እየተጠቀሙ በቴዲ እና በደጋፊዎቹ ላይ እየወሰዷቸው ያሏቸውን ዕኩይ ተግባራት ለማሳየት ነው፡፡ ከመጀመሪያው ጀምሮ ከኮካ ኮላ ጋር የተደረገውን አጠቃላይ ስምምነት ብልግና በተቀላቀለበት መልኩ እየሳቁ ሲመለከቱት ቆይተዋል፡፡ እንዲቀጥልም ፈቅደዋል፡፡ እንዲህም ብለው ነበር፣ “ቴዲ ከልቡ ጥረት ያድርግ እና ቆንጆ የሙዚቃ ስራ ይዞ ይቅረብ“፣ መዳፎቻቸውን በማፋተግ እንዲህ ብለው ነበር፣ “ጥሩ አድርገን በመበቀል ሊረሳው በማይችል መልኩ አርአያ የሚሆን ትምህርት እንሰጠዋለን“፡፡ በእነዚህ የእኩይ ምግባር አራማጆች የደም ስሮች ውስጥ ጥላቻ እና በቀልተኝነት ተዋህደዋል፡፡

በመጨረሻዋ ደቂቃ በኮካ ኮላ በኩል የበቀል እርምጃቸውን ወስደዋል፡፡ (ኮካ ኮላ እ.ኤ.አ በ2013 ሶስተኛውን የጠርሙስ ፋብሪካ በድሬ ዳዋ ከተማ ያጠናቀቀ መሆኑን ልብ ይሏል፡፡) ኮካ ኮላ ገበያውን በኢትዮጵያ ለማስፋት ከፈለገ የቴዲ አፍሮን የዓለም እግር ኳስ ዋንጫ ማድመቂያ ሙዚቃ መልቀቅ የለበትም፡፡ ምስኪኑ ኮካ ኮላ በሰይጣኖች እና በቴዲ አፍሮ መካከል በተያዘው ጉዳይ ላይ መሳሪያ በመሆን የይስሙላ መወዛወዝን ይዞ ቀትረ ቀላል ሆኖ ይገኛል፡፡

በእርግጥ ያ ሁሉ በገዥው አካል እየተደረገ ያለው በሸፍጥ የተሞላ እርባና የለሽ ድርጊት በቴዲ አፍሮ ስብዕና ላይ የሚያመጣው ነገር አይኖርም፡፡ ቴዲ በሚመስጠው ቅላጼው “ፍቅር ሁሉን ያሸንፋል” የሚል ሙዚቃውን ማሰማቱን ይቀጥላል፡፡ “ሙሉ ይቅርታን ከማድረግ በላይ በቀል የለም” የሚለውን መርህ ነው የሚከተለው፡፡ እሱን ጥፋተኛ ያደረጉትን ይቅርታ ያደርግላቸዋል (ጃህ ያስተሰርያል!)

በኢትዮጵያ ላለው ወሮበላ ዘራፊ ቡድን ማንኛውም ተመልካች የቴዲ አፍሮን ስም ጥላሸት ለመቀባት፣ ለማበሳጨት እና የአገሪቱ ብሄራዊ የአንድነት እና የክብር መገለጫ ምልክት የሆነውን ጀግና ታዋቂ የኢትዮጵያ የፖፕ ሙዚቃ አቀንቃኝ ስሜት ለመጉዳት በሚያደርጉት እርባና የለሽ የስነ ልቦና ጦርነት ላይ እንግዳ ሊሆንበት አይችልም፡፡ ለበርካታ ዓመታት እነዚህን ቆሻሻ የማታለል ድርጊቶቻቸውን በተቀናቃኞቻቸው ላይ ሲፈጽሙ ቆይተዋል፣ አሁንም ይህንን እኩይ ምግባራቸውን በተጠናከረ መልኩ ይቀጥሉበታል፡፡

እውነታው ግን የቴዲ አፍሮ የኪነ ጥበብ ሙያ ለኢትዮጵያውያን እና ኢትዮጵያውያት የማይሞተውን ጠንካራ ፍቅር አሳይቷል፡፡ በሁሉም ሙዚቃዎቹ እና ግጥሞቹ ቴዲ የኢትዮጵያን ክብር ከፍ አድርጎ አሳይቷል፣ እንዲሁም ለወሮበላ ዘራፊዎች እና ለከሀዲዎች እውነታውን ነግሯቸዋል፡፡ የእርሱ ሙዚቃ፣ መዝሙሮች እና ግጥሞች የአውዳሚነት ጥረቶችን በማዳከም በኩል የኢትዮጵያን ህዝብ እምነት እና ሞራል ከፍ በማድረግ ውጤታማ ክስተቶችን ፈጥረዋል፡፡ ቴዲ በግጥሞቹ እንዲህ በማለት አውጇል፣ “ያዙት፣ ጠበቅ አድርጋችሁ ያዙት! እርስ በእርሳችን ይቅርታ ካደረግን እና ከተፋቀርን የኢትዮጵያ ትንሳኤ ቅርብ ነው፡፡“

ቴዲ ተያስተሰርያል በሚለው አልበሙ በቡድን የወሮበላ ስብስብ ወንጀለኞች የተያዘውን ዙፋን አጋልጧል፡፡ መዝሙሩን በመጠቀም በኢትዮጵያ ውስጥ የሚኖሩ ሁሉም የጎሳ መሰረት ያላቸው ህዝቦች በስምምነት፣ በሰላም እና በፍቅር በአንድ ኢትዮጵያዊነት ጥላ ስር በህብረት እንዲኖሩ አዚሟል፡፡ ከፍተኛ ዋጋ ያለውን የሙዚቃ ክህሎት በመጠቀም የክርስቲያን እና የእስልምና እምነት ተከታዮች እጆቻቸውን በማጣመር በአንድነት በሰላም እና በፍቅር እንዲኖሩ አስተምሯል፡፡ ቴዲ የታደለውን የዓላማ ጽናት ለእኩይ ምግባር እንዲሸጥ ለማድረግ ለመቁጠር ከሚያዳግተው በላይ በርካታ ሀብት እና ሽልማት ቀርቦለት ነበር፡፡ ሆኖም ግን በተገኘው አጋጣሚ ሁሉ ነብሱን ለወሮበላ ዘራፊዎች ለመሸጥ እንደማያስብ ጽኑ ተቃውሞ አሳይቷል፡፡

ቴዲ አፍሮ በእርሱ የትውልድ ዘመን ካሉ የጥበብ ባለሙያዎች ሁሉ የበለጠ እና የላቀ ተነሳሽነት ያለው ወጣት ከያኒ ነው፡፡ ቴዲ በብዙ ሚሊዮን የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን/ት ወጣቶችን ቀልብ በመሳብ ዴሞክራሲ፣ ነጻነት እና ሰብአዊ መብቶች በአንዲት ኢትዮጵያ እንዲጠበቁ እና እንዲከበሩ አነቃንቋል፡፡ በአሁኑ ጊዜ የእኩይ ምግባር አራማጆቹ በሙዚቃው ያሳየውን አርበኝነት ለመበቀል አሁን ያዘጋጀው ሙዚቃ እንዳይለቀቅ በመከልከል “ዋጋ” እንዲከፍል እያደረጉ ነው፡፡ የእውነትን መዝሙርን በምንም ዓይነት መልኩ ማገድ እና ጸጥ ማድረግ አይቻልም፡፡

ቴዲ የሚሸጥ ዕቃ አይደለም! ቴዲ በኮካ ኮላ ወይም በወሮበላ ዘራፊ ቡድን ባለብዙ ቢሊዮን ገንዘብ ባለቤት ቱጃሮች የሚገዛ ሸቀጥ አይደለም፡፡ እርሱን ለማዋረድ እና ለመዘለፍ መሞከር ይችላሉ፡፡ ቀላሉ እውነታ ግን ቴዲ በእራሱ እና በሀገሩ ላይ የራስ ደጀን ተራራን የሚያህል ኩራት እና ክብር ያለው ትንታግ ወጣት መሆኑን ያለመገንዘባቸው ነው፡፡ ወሮበላ ዘራፊዎች ከህዝብ በሰረቁት እና በዘረፉት ኃብት ምንም ያህል ኃብት ቢያከማቹ ማጅራት መችዎች ለዘላለም የሚኖሩ ወሮበላ ዘራፊዎች፣ በጥባጮች እና ማጅራት መችዎች ሆነው ይቀራሉ፡፡ ይህም የሚያዋርድ የቋንቋ ቃላትን መደርደር አይደለም፡፡ ይህ እንደ ቀትር ጸሐይ የበራ ኃቅ ነው!

እባካችሁ ቴዲ አፍሮ በእራሱ እና በእናት ሀገሩ ላይ ኩራት እና ፍቅር ያለው ትንታግ ወጣት በመሆኑ ምክንያት ብቻ አትጥሉት! እርሱን አትጥሉት፣ ምክንያቱም የሀገር ምልክት ነው፡፡ እርሱን አትጥሉት፣ ምክንያቱም የሀገር አርበኛ ነው፡፡ ምንም ማድረግ አይችልም፡፡ እንደዚያ ሆኖ ነው የተወለደው!

በኢትዮጵያ ያለው እውነተኛው ቴዲ አፍሮ እንጂ የኮካ ሸቀጥ አይደለም!

ዓለም እና አብዛኛው የዓለም ህብረተሰብ እንዲሁም የዓለም የእግር ኳስ ፌዴሬሽን ቴዲ አፍሮን ይፈልገዋል፡፡ ቴዲ የአፍሪካ የሙዚቃ ሊቅ ነው፡፡ የእርሱ የሙዚቃ ግጥም “ፍቅር ሁሉን ያሸንፋል” በሚል መርህ ላይ የተዋቀረ ነው! አፍሪካውያን/ት ግጥሞቻቸውን እና የሙዚቃ ፍቅሮቻቸውን ወደ አንድነት መድረክ እንዲያመጡ እያደረገ ነው፡፡

ቴዲ በአሁኑ ጊዜ በኢትዮጵያ ታዋቂው የጥበብ ባለሙያ ነው ምክንያቱም የእርሱ ሙዚቃ ህዝቡን ወደ አንድነት እያመጣ ነው፡፡ ቴዲ አፍሮ በኢትዮጵያውያን/ት እና አፍሪካውያን/ት ፍቅርን፣ ሰላምን፣ አብሮነትን እና መልካም ነገርን ሁሉ ይዘምራል፡፡ የእምቢተኝነት መዝሙሮችን ይዘምራል፡፡ ስለእርቅ አስፈላጊነት፣ መግባባት እና ይቅርባይነት ይዘምራል፡፡ አዲሲቷን ኢትዮጵያ ለመገንባት አጠንክረው ለሚሰሩ ሀገር ወዳዶች ሁሉ የስራ መዝሙሮችን ይዘምራል፡፡ ስለኢትዮጵያ ተፈጥሯዊ ማራኪነት እና ስለህዝቧ ደግነት ይዘምራል፡፡ ቴዲ አፍሮ በአፍሪካ ላይ ስላለው ፍቅር ይዘምራል፡፡

የቴዲ አፍሮ ሙዚቃ ህይወትን የበለጠ አስደሳች አድርጎታል፡፡ የዓለም ህዝብ ቴዲ አፍሮ ሰለፍቅር ሲዘምር እንዲያዳምጠው ማየት እፈልጋሁ፡፡ በማያቋርጥ አምባገነንነት መዳፍ ስር ወድቃ ህይወት አልባ እና ደስታ ከራቃት አገር ይልቅ የቴዲ አፍሮ ሙዚቃ ህይወትን እና ደስታን ይጨምራል
ቴዲ አፍሮ እውነተኛ ነገር ነው! ቴዲ አፍሮ እውነተኛ ኢትዮጵያዊ ነው!

ቴዲ አፍሮ በቅርብ ጊዜ ያሳተመው “ጥቁር ሰው” የተባለው አልበሙ ኢትዮጵያ እ.ኤ.አ በ1896 በኢጣሊያ ቅኝ ገዥ ወራሪ ኃይል ላይ የተቀዳጀችውን ድል የሚዘክር ነው፡፡ ያ አንጸባራቂ ድል በአፍሪካ እና በዓለም ታሪክ ላይ ጉልህ ምዕራፍን ይዞ ይገኛል፡፡ የአውሮፓ ቅኝ ገዥዎች አፍሪካን እንደ ቅርጫ ስጋ ለመከፋፈል እና የአፍሪካን ህዝቦች በባርነት በመያዝ ጥሬ ሀብቷን ለመዝረፍ በማቀድ በበርሊን ከተማ ከተደረገው ጉባኤ ሁለት ዓመታት ባልበለጠ ጊዜ ውስጥ በኢጣሊያን እና በኢትዮጵያ መካከል በተደረገው የመጀመሪያው ጦርነት የኢትዮጵያው ዳግማዊ አጼ ምኒልክ የኢጣሊያንን ወራሪ ወታደሮች በአድዋ ጦርነት ላይ አይቀጡ ቅጣት በመቅጣት የሞቱት ሞተው የተረፉት እግሬ አውጭኝ በማለት ወደመጡበት እንዲመለሱ አድርገዋል፡፡ የአድዋ ጦርነት የአውሮፓ ኃያል በታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ በአፍሪካ ወታደሮች ጉልበት ስር እንዲንበረከክ የተገደደበት ጊዜን ያስታውሳል፡፡ ፋሽስት ኢጣሊያ እንደገና እ.ኤ.አ በ1935 ኢትዮጵያን በቅኝ ግዛትነት ለመያዝ ሁለተኛውን የኢጣሊያን እና የኢትዮጵያን ጦርነት ለኮሰች፡፡ በዚህም ጦርነት ለዘላለም ሊረሱት የማይችሉት የሽምቅ ውጊያን ሽንፈት ተከናንበው ወደ አገራቸው ተመልሰዋል፡፡ ኢትዮጵያ (በአፍሪካ ከሌላዋ ላይቤሪያ በስተቀር) ነጻነቷን ጠብቃ የቆየች ከቅኝ ግዛትነት ነጻ የሆነች አገር ሆና እንድትቆይ አድርጓታል፡፡ ቴዲ አፍሮ ስለፍርኃት የለሽ መሪዎቿ እና ነጻነታቸውን እና ሉዓላዊነታቸውን ላለማስደፈር በቀስት እና በደጋን እንዲሁም ኋቀር በሆኑ ጠብመንጃዎች በመታገዝ ብቻ ሳይሆን በነበራቸው ኩራት እና ወኔ በጀግንነት ተዋግተው የሀገራቸውን ነጻነት እና ህልውና ላስከበሩት ተራ ኢትዮጵያውያን ጀግኖችም ዘምሯል፡፡

በቴዲ እና ልዩ በሆኑት የኪነ ጥበብ ስራዎቹ ኮርቻለሁ፡፡ ለኢትዮጵያ ልዩ ባህል እርሱ ላበረከታቸው እጅግ መጠነ ሰፊ በሆኑ አበርክቶዎቹ ሁሉ በጣም ኮርቻለሁ፡፡ በሙዚቃ ስራዎቹ አማካይነት ፍቅር፣ አንድነት እና በህዝቦች መካከል ብሄራዊ ዕርቅ እንዲወርድ ባደረጋቸው እልህ አስጨራሽ ጥረቶች ላይ እጅግ ኮርቻለሁ፡፡ ቴዲ ልዩ የመንፈስ ጽናት ያለው እና የውርደትን ትጥቅ ያስፈታ ትንታግ ከያኒ ወጣት ነው፡፡ የእርሱን ዝና እና ክብር ለማንቋሸሽ በተከታታይነት ዘመቻ ሲያደርጉበት ምንም ዓይነት ምላሽ አይሰጣቸውም፡፡ በእርግጠኝነት እንዲህ ብቻ ይላል፣ “ፍቅር ሁሉንም ያሸንፋል፡፡“ በጥላቻ የተሞሉ የእኩይ ምግባር አራማጆች ፍቅር ሁሉንም ያሸንፋል ብሎ የተነሳን ሰው በምንም ዓይነት መልኩ ሊያሸንፉ አይችሉም፡፡

አሁን በህይወት የሌለው መለስ እ.ኤ.አ በ2008 በሰው ላይ የመኪና አደጋ አድርሶ አምልጧል በሚል በውሸት የተቀነባበረ የሸፍጥ ክስ ሳቢያ ቴዲ አፍሮን ወደ እስር ቤት በወረወረው ጊዜ በቴዲ ጎን ቆሜ በዓለም ህዝብ የሕሊና ፍርድ ቤት ስከራከር ነበር፡፡ እንደዚሁም ቴዲ አፍሮ ፈጽሟቸዋል በሚል የፍብረካ ወንጀሎች በቁጥጥር ስር ውሎ ክስ እንዲመሰረትበት መለስ ያስተላለፈውን ትዕዛዝ የተቀነባበሩ 10 አገር ከመውደድ ጋር ተያይዞ የሰራዉን የ “ወንጀል ክሶች” ዝርዝር መዝግቤ ይዣለሁ፡፡ የመለስ እኩይ የሙት መንፈስ በቴዲ ግጥሞች በተገለጹ እውነቶች እና እምነቶች ሲወጋ እና ሲባንን ይኖራል፡፡

ቴዲ እ.ኤ.አ በ2010 ወደ ሎስ አንጀለስ በመጣበት ወቅት የእርሱን የሙዚቃ ትርኢት ተመልክቸ ነበር፡፡ የሙዚቃ ትርኢቱ አስደናቂ ነበር፡፡ የቴዲ የሙዚቃ ትርኢት ወጣት በነበርኩበት ጊዜ እ.ኤ.አ በ1970ዎቹ መጨረሻ አካባቢ በመጀመሪያው እረድፍ ላይ ቆሜ ያየሁትን የታላቁን ቦብ ማርሌይን ካያ እና የህይወት ግብግብ ጎዞ/Kaya and Survival tour በሚል ርዕስ የቀረበውን ሙዚቃዊ ትርኢት እንዳስታውስ አደረገኝ፡፡ ቦብ ማርሌይ በአፍሪካ ነጻነት እና በፓን አፍሪካኒዝም ላይ እንደነበረው ፍቅር ሁሉ ቴዲ አፍሮም በተመሳሳሳይ መልኩ በነጻነት፣ በአንድነት፣ ዕርቀ ሰላም በማውረድ እና በአትዮጵያ ህዝቦች ላይ ፍቅር እንዲሰፍን ይፈልጋል፡፡ እንደ ማርሌይ ሁሉ የቴዲ ሙዚቃም ቀስቃሽ፣ አስደማሚ እና ልብ አንጠልጣይም ነው፡፡ እንደ ማርሌይ ሁሉ ቴዲም ስለፍቅር፣ ሰላም፣ ተስፋ፣ እምነት፣ ለጋሽነት፣ ፍትህ፣ ዕርቅ፣ መግባባት እና ይቅርታ አድራጊነት ይዘምራል፡፡ እንግዲህ እነዚህ ነገሮች ናቸው የቴዲ አፍሮን የሙዚቃ የቅላጼ ኃይል በኢትዮጵያውያን/ት ልብ እና ልቦና ውስጥ ዘልቀው በመግባት የተስፋ ማጣት ቁስልን፣ ማለቂያ የሌለውን ጭቆና እና ኢትዮጵያን ከአምባገነንነት መቃብር ለማዳን ለቀዶ ጥገናው ስራ በመስፊያ ክርነት እያገለገሉ ያሉት፡፡ ቴዲን በኢትዮጵያ ውስጥ ስለፍቅር፣ ሰላም እና ፍትህ ከመስበክ እና ከመዘመር የሚያግደው ምንም ምድራዊ ኃይል የለም፡፡

ቴዲን የኢትዮጵያ ጅግና የስነ ጥበብ ባለሙያ እና የእራሴም ግላዊ ጀግና አድርጌ እቆጥረዋለሁ!

ዓለም የእኛ ናት የኮካ አይደለችም፡፡ አንድ ኮካ ኮላን በአንድ ሰው ማስወገድ፣ አንድ ኮካ ጠርሙስ በአንድ ጊዜ ማስወገድ አለብን!

የእኔን ሳምንታዊ ትችቶች ለበርካታ ዓመታት በመከታተል ላይ ለሚገኙት በሚሊዮን የሚቆጠሩ አንባቢዎቼ እኔን እዲቀላቀሉኝ እና “ኮካን ከመጠቀም እንዲያስወግዱ” የአክብሮት ጥሪየን አቀርባለሁ!

ኮካ ኮላ በጨለማ እንደሚካሄድ የኃይማኖት ክብረ በዓል የሻማ ብርሀን ይዘን ለተቃውሞ ሰላማዊ ሰልፍ ብንወጣ ጉዳዩ አይደለም፡፡ ኮካ ኮላ ስለእኛ ሞራል ዝቅጠት ጉዳይ ደንታ የለውም፡፡ የኮካ ኮላ ዋና ጉዳይ ከሁሉም በላይ ስለትርፍ እና ኪሳራ ማሰላሰል ብቻ ነው፡፡ ኮካ ኮላ ከ200 በላይ በሚሆኑ አገሮች ከ30 ቢሊዮን በላይ የሚሆኑ ዓለም አቀፍ ሽያጮችን ያካሂዳል፡፡ በየዓመቱ በቢሊዮን የሚቆጠሩ ዶላሮችን ለገበያ ማስተዋወቂያ ዘመቻ ወጭ ያደርጋል፡፡ ኮካ ኮላ በውል ሊገነዘበው የሚችለው ብቸኛው ቋንቋ የትርፍ እና ኪሳራ ቋንቋ ነው፡፡

በአንድ ጊዜ አንድ ሰው ኮካ ኮላን መግዛት እና መጠቀምን ቢያቆም እና የ114 የኮካ ኮላ ምርት ውጤቶችን መግዛት እና መጠቀምን ብናቆም ዓለማችንን ከኮካ ኮላ መዳፍ ስር በ114 ቀናት ውስጥ ማላቀቅ እንችላለን፡፡

በኢትዮጵያ ያሉ አንባቢዎቼ ኮካ ኮላ መጠጣትን እንዲያቆሙ በአክብሮት እጠይቃለሁ፡፡ የእራሳቸው “የኮካ መጠቀም ማስወገጃ ቀን” እንዲኖራቸው እጠይቃለሁ፡፡ ሁልጊዜ ኮካ ሲቀርብ አሻፈረኝ አልፈለግም አንዲሉ !!!

ይህ የማስወገድ ስልት በኮካ ኮላ ላይ ብቻ የተወሰነ መሆን የለበትም፡፡ ስለኢትዮጵያ ብሄራዊ ኩራት ጭምር ነው፡፡ አገራችንን ከሶዳ ቸርቻሪ እና ከወሮበላ ዘራፊዎች ማላቀቅ አስፈላጊ ነው፡፡

አንድ የካካ ኮላ ጠርሙስን ባንድ ሰው እንዋጋ እላለሁ፣ አንድ ሰው ኮካ ኮላ በአንድ ጊዜ ማስወገድ ይቻላል! እምቢ ኮካ አልፈልግም

ኮካ ኮላ እንዲህ በማለት ጉራዉን ይነዛል ፣ “ዓለም የእኛ ናት!“ አኛ ደግሞ ለ ኮካ ኮላ ኢትዮጵያ የእኛ መሆኗን ማሳየት አለብን!

በመጨረሻም የእኔ ኮካ ኮላን መጠጣት የማስወገድ ዓላማ ቴዲን ነጻ እንዲያደርገው በኮካ ኮላ ላይ ውጥረት ለመፍጠር አይደለም፡፡ እንደዚሁም ደግሞ ከጀርባ መጋረጃ ሆኖ የኮካ ኮላን እጅ ለሚጠመዝዘው ለአንደበተ ድሁሩ የገዥ አካል እውነተኛውን ነገር እስከ አፍንጫው ለመንገርም አይደለም፡፡ ይህንን የማደርገው ኢትዮጵያዊ በመሆኔ ስለሚሰማኝ ክብርና ሞገስ ስለማስብ ብቻ ነው፡፡

ተባበሩኝ እባካቸሁ ለክብራችሁ
ተባበሩኝ ለክብራችን
ውርደት እስከመቼ ተሸክምን እንችላለን?
ባንደበታችን መናገር ባንችል
ባንደበታችን የሚገባዉን ማስቆም አንችላለን ::

ተባበሩኝ ወገኖች ጀግኖች ለክብራችን !
ኮካ ኮላ ነው በሉ የሚያስጠላ፥ የሚያጣላ::

በግሌ የምለው አንዲህ ነው፥

ኮካ ኮላ ለዓለም አቀፉ የእግር ኳስ ዋንጫ ጨዋታ ካዘዛቸው 32 አገራዊ ልዩ ሙዚቃዎች መካከል 31ዱን ከለቀቀ እና የታላቂቱ የኢትዮጵያን ልዩ ሙዚቃ አሽቀንጠሮ ከጣለ በበኩሌ ኮካ ኮላን የምለው “ተምዘግዝጋችሁ ገሀነም ግቡ” ነው!!!”

ኮካ ኮላ፥ የሚያስጠላ የሚያጣላ!!!

ኢትዮጵያ በክብር ለዘላለም ትኑር!
ሰኔ 10 ቀን 2006 ዓ.ም

የትግራይን መስቀል ስለመሸከም ….ከጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ

$
0
0
ተመስገን ደሳለኝ)

ተመስገን ደሳለኝ)

…ዕለቱ የሁለት ሺ ሶስት ዓመተ ምህረት የመስቀል በዓል የተከበረበት ማግስት፤ ሰሜናዊቷ የኤርትራ አዋሳኝ ወልቃይት ገና ከእንቅልፏ ሙሉ ለሙሉ ባለመንቃቷ፣ እስከ አፍንጫቸው የታጠቁ ጎፈሪያቸው የተንጨ(ባረረ ፋኖዎች በውስጧ ካሉ ተቋማት ወደ አንዱ እያመሩ ስለመሆኑ የጠረጠረች አትመስልም፤ ከኤርትራ የተነሱት ፋኖዎች መዳረሻ በወረዳዋ ታዋቂ የሆነው አወርቅ የመጀመሪያና ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት በመሆኑ፤ ማንም ልብ ሳይላቸው ልክ እዚያው እንደደረሱ፣ ከፊሎቹ በሰለጠነ ወታደራዊ ስልት ትምህርት ቤቱን ከአጥር ውጪ በመክበብ ድንገተኛ ጥቃት የሚሰነዝር ኃይል ከመጣ ለመከላከል ሲያደፍጡ፤ የተቀሩት ደግሞ ወደ ውስጥ በመግባት በግቢው የሚገኙ መምህራን ሜዳው ላይ እንዲሰበሰቡ ቀጭን ትዕዛዝ አስተላለፉ፤ በጥቂት ደቂቃዎችም ውስጥ ሁሉም በተባለበት ቦታ ተሰበሰበ፤ እያንዳንዷን እንቅስቃሴ በዕቅዱ መሰረት መፈፀሙን በጥንቃቄ ሲከታተል የነበረው የቡድኑ መሪ በቅድሚያ ስለራሱና ጓደኞቹ ማንነት እና ስለወከሉት ድርጅት አጭር ማብራሪያ ከሰጠ በኋላ፣ የትግሉን ዓላማ በስፋት አብራርቶ አስረዳ፤ ሌሎች ጓዶቹም የፖለቲካ ፕሮግራማቸውን ዋና ዋና ርዕሶች የሚገልጹ በአማርኛና ትግርኛ ቋንቋ የተዘጋጁ በራሪ ወረቀቶችን የማደል ስራቸውን በማጠናቀቃቸው እንደአመጣጣቸው በሽምቅ ተዋጊ ስልት ከአካባቢው ተሰወሩ፡፡ ይህ በሆነ በአስራ ሁለተኛው ቀን (መስከረም 30) ደግሞ እዛው ወረዳ ወደሚገኝ ሌላ ትምህርት ቤት ለተመሳሳይ ዓላማ ድንገት ተመልሰው መጥተው ነበር፤ ሆኖም መንገድ ላይ ካደፈጡ ፖሊሶችና ታጣቂዎች ጋር ፊት ለፊት ተገጣጥመው በተፈጠረው ግጭት ሳቢያ ከእነርሱ ወገን አንድ ሲሰዋ፤ ከፖሊስ አባላት አንድ ቆስሏል፤ አንድ መምህርም በገዛ ቤቱ በተቀመጠበት በተባራሪ ጥይት ቆስሏል፤ ፋኖዎቹም የዚያ ቀን ዓላማቸው ከሽፎ ወደመጡበት የኤርትራ በርሃ ተመልሰው ለመሄድ ተገድደዋል…Temesgen Desalegn “Fact” Ethiopian Amharic newspaper editor

ፊታችሁን ወደ ሰሜን…
ከወዳጆቼ ግርማ ሰይፉና በላይ ፍቃዱ ጋር መቀሌን ለመጎብኘት የነበረን ዕቅድ በተለያዩ ምክንያቶች እየተሰናከለ፤ መልሶ እየተወጠነ ጥቂት ለማይባሉ ወራት ሲጓተት ቆይቶ፣ በግንቦት መጨረሻ ዕለተ-አርብ ምሽት ላይ፣ ህወሓት እነ ለገሰ አስፋውን በኃይል አባርሮ በእጁ ወደአስገባት ሞቃታማዋ የትግራይ ርዕሰ-መስተዳድር መቀመጫ ደረስን፤ ከ1983 ዓ.ም ወዲህ ከባድ ፖለቲካዊ ጉዳዮች ተፈጭተው የሚጋገሩባትን፣ የአጼ ዮሀንስ ከተማ ለአራት ቀናት ተቆጣጠርናት ስናበቃ፤ ‹ከእግር እስከ ራሷ…› ለማለት ባያስደፍርም፣ የቻልነውን ያህል በጉብኝት አካለልናት፤ በተናጠልም መነሻዬን ‹ሮሚናት› አደባባይ (መሀል እምብርቷን) አድርጌ በአራቱም አቅጣጫ ለመቃኘት ሞክሬያለሁ፤ በዋናነት ትኩረቴን የሳበው ከሰማዕታቱ ሐውልት በስተሰሜን ተንጣሎ የሚገኘው መንደር ነው፤ መንደሩ በዘመናዊ መኖሪያ ቤቶች ተውቦ ሲታይ፣ የደቡብ አፍሪካዋ ጽዱ ከተማ ኬብ-ታዎን ያሉ ቢመስልዎ ስህተቱ የእርስዎ አይሆንም፤ ስለምን ቢሉ? እየተመለከቱ ያሉት ስነ-ሕንፃ ውበት እጅግ በተራቀቁ ዘመን አመጣሽ የግንባታ ቁሳቁሶች የተንቆጠቆጠ መንደር ነውና፡፡ ወደቦታው ይዞኝ የሄደው ጎልማሳ የባጃጅ አሽከርካሪ ‹‹በትግራይ ክልል ባሉ 46ቱም ወረዳዎች በተለያየ ጊዜ በኃላፊነት ከተመደቡ አስተዳዳሪዎች ውስጥ አብዛኛዎቹ እዚህ መኖሪያ ቤት አላቸው›› ሲለኝ ግን ማመን ቢያዳግተኝም አድናቆቴ ወደ ከፍተኛ ድንጋጤ ተቀይሯል፤ ምክንያቱም ቤቶቹ በመንግስት ደሞዝ ሊሰሩ ቀርቶ፣ ሊታሰቡ እንደማይችሉ በግልፅ ያስታውቃሉና ነው፤ ታዲያ! ይህ እንዴት ሊሆን ቻለ? ምናልባት የአስተዳዳሪዎቹ ደሞዝ እንደ አክሱማውያን ዘመን በወቂት (በወርቅ ድንጋይ) ይሆን እንዴ?
የሆነው ሆኖ አንጋፋዎቹ ‹የታገለ-ያታገለ፣ በድል አጥቢያ አርበኝነት ያገለገለ፣ በሀገር ሀብት እንዳሻው የመምነሽነሽ መብት አለው› እንዲሉ፣ ነገሩ ወዲህ ነው፡፡ አገሬውም ይህንን እውነታ አብጠርጥሮ በማወቁ አካባቢውን ‹‹ሙስና ሰፈር›› ብሎ እንደሚጠራው ስሰማ፣ ጎልማሳው የነገረኝን ወደማመኑ ጠርዝ ተገፋሁ፡፡ መደበኛ ባልሆነ መልኩ የተወያየኋቸው በተለያየ ዕድሜ ላይ የሚገኙ በዛ ያሉ የከተማዋ ነዋሪዎችም ባለንብረቶቹ የህወሓት ካድሬዎች እንደሆኑ መስማታቸውን አረጋግጠውልኛል፡፡ በይበልጥ ደግሞ ሁለት ልጆቻቸውን በትግሉ እንዳጡ ያወጉኝ አንድ አዛውንት ምንም እንኳ እተባለው አካባቢ ሄደው ቤቶቹን በአይናቸው አለማየታቸውን ባይሸሽጉኝም፣ በተሰበረ ስሜትና ምሬት በዋጠው ድምፅ ‹‹እነርሱ በእኛ ልጆች ደም ተረማምደው፣ ለድል ከበቁ በኋላ ዓላማቸውን ትተው የሀገርን ሀብት በመዝረፍ ራሳቸውንና ዘመዶቻቸውን ባለፀጋ ማድረግ እንደቻሉ በሰማሁ ቁጥር፣ ልጆቼ የተሰዉት በደርግ ወታደሮች ጥይት ሳይሆን በገዛ የበረሃ ጓዶቻቸው ክህደት እንደሆነ አድርጌ በማሰብ በቁጭት ስለምብሰክሰክ ሀዘኑ እንደ አዲስ ያንገበግበኛል›› ሲሉ መስማት ምንኛ እንደሚያሸማቅቅ ማንም ለመገመት አይከብደውም፡፡

የዚህ አይን ያወጣ ዘረፋ መነሾም ድርጅቱ በተለይም የ1993ቱን ‹ዳግማዊ ህንፍሽፍሽ› ተከትሎ ያጋጠመውን የታማኝ ሰው እጥረት ለማሟላት መስፈርቱ ‹‹ህወሓትን እንደ ግል አዳኝ›› መቀበል ላይ የሚያተኩር እንጂ፤ የስነ-ምግባር ጉድለት ኖረ አልኖረ አሳሳቢው ባለመሆኑ እንደነበረ ይነገራል፡፡ በዚህ ድምዳሜም የቀድሞ አመራሮቹ ጭምር እንደሚስማሙ አስተውያለሁ፡፡ እውነታውን የሚያውቀው የከተማዋ ነዋሪም ቢሆን፣ ደፍሮ ህወሓትን ‹‹ሌባ!›› ብሎ ባያወግዝም፤ ተቃውሞውን ለመግለፅ መንደሩን ‹‹ሙስና ሰፈር›› በማለት መሰየሙ በራሱ አንድ ማሳያ ነው፡፡ መቼም በመቀሌ እልፍ አእላፍ ሰላዮች ከመሰግሰጋቸውም ባለፈ፣ ከምሁር እስከ ሊስትሮ፣ ከነጋዴ እስከ አርሶ አደር በጠንካራ ጥርነፋዊ መዋቅር የተጠፈሩባት ከመሆኗ አኳያ፣ ግንባታውንም ሆነ ነዋሪው የሰጠውን ስያሜ፤ ትላንት መለስ ዜናዊ፣ ዛሬ ደግሞ እነ አባይ ፀሀዬ ‹አልሰሙ ይሆናል› ብሎ ማሰቡ “ፀሀይ በምዕራብ ትወጣለች” አይነት ጉንጭ አልፋ ክርክር ነው ብዬ አምናለሁ፡፡

ሌላው የከተማዋ ‹‹ጥቁር ሐውልት›› ተብሎ ሊጠቀስ የሚችለው፣ ጋዜጠኛ ዮናስ በላይ በ2003 ዓ/ም በወርሃ ነሐሴ በታተመችው ‹‹ፍትሕ›› ጋዜጣ ላይ (በቅርቡ ባሳተመው ‹‹ወያኔዎቹና ሽፍቶቹ›› በተሰኘ መጽሐፉም አካቶታል) ‹‹ገረቡቡ-የመቀሌው አፓርታይድ መንደር›› በሚል ርዕስ ካስነበበን ‹‹የግንቦት ሃያ ፍሬ›› ጋር የሚያያዝ ነው፡፡ ዮናስ በጽሑፉ እንደገለፀው መንደሩ የተመሰረተው በድፍን መቀሌ በምቾቱ የተሻለ በሚባለው መልከዓ-ምድር ላይ ነው፤ ባለቤቶቹ የህወሓት ማዕከላዊ ኮሚቴ አባላት እና ጥቂት ባለሀብቶች መሆናቸውንም ሆነ፣ የደቡብ አፍሪካውን የጭቆና ስርዓት የሚያስታውሰው መጠሪያ ስሙ ከመንደሩ አጎራባች ያሉ የኤስ.ኦ.ኤስ ትምህርት ቤት ተማሪዎች እንዳወጡለት ወዳጃችን ዮናስ ጨምሮ ማስነበቡ አይዘነጋም፡፡ …እነሆም መቀሌ እንዲህ ነች፤ በጉራማይሌ ገፅታ የተገነባች፤ ህወሓታውያኑን በምቾት የምትንከባከብ፤ ሰፊውን ሕዝቧን ደግሞ ምድራዊ ፍዳ የምታስቆጥር፡፡

በነገራችን ላይ ከተማዋ ከአዲስ አበባ ቀጥሎ መግዘፏን አስተውያለሁ፤ ይህ ግን የፈረደበት ድፍን ትግራዋይን በተለየ መልኩ ተጠቃሚ ሆኗል እንደማለት አይደለም፤ ዳሩ የዚህ አይነቱን የሕንፃ ጋጋታ ከክልሉ ውጪ ያሉ ኢትዮጵያዊያን የአድሎአዊነት ማሳያ አድርገው ሊወስዱት እንደሚችሉ አስባለሁ፡፡ ጥያቄው ግን ይህ አይደለም፤ ይልቁንም ሰማይ ጠቀሶቹ ፎቆቿም ሆኑ ዘመናዊ ሆቴሎቿ አሊያም ቤተ-መንግስትን የሚያስንቁ መኖሪያ ቤቶቿ ለተርታው ነዋሪ ምን ፈየዱለት? የሚል እንጂ፡፡ እውነት እንነጋገር ከተባለም ይህ ኩነት በዋናነት የሚያመላክተው መቀሌ፣ በህወሓት መካከለኛና ከፍተኛ ካድሬዎች፤ እንዲሁም እነርሱን በተጠጉ ባለሀብቶች ወደ ሀጢአን ቅጥርነት እየተቀየረች መሆኗን ነው፤ ይህን ለማለት ያስደፈረኝ አንድም ብዙዎቹ ግንባታዎች ግለሰባዊ እንጂ መንግስታዊ አለመሆናቸው ሲሆን፤ ሁለትም ሕንፃዎቹ መኖሪያ ቤቶች እና ሆቴሎች በመሆናቸው ነው (እያወራን ያለነው ስለኢንዱስትሪዎች አይደለም)፡፡ እናሳ! ይህ አይነት ግንባታ ለንብረቱ ባለቤቶች ካልሆነ በቀር ለትግራይ ሕዝብ ምኑ ነው? …ርግጥ ነው እነዛ ለ17 ዓመታት ያህል የሰው ልጅ ይቋቋመዋል ተብሎ የማይታሰብ መከራ እየተቀበሉ ተራሮቹን ያንቀጠቀጡ ታጋዮች፤ ከድሉ በኋላ እሳት የላሱ፣ የመርካቶ ነጋዴን በብልጠት የሚያስከነዱ ሆነዋል፡፡
እዚህ ጋ ሳይነሳ የማይታለፈው ሌላው ነጥብ የከተማዋ ነዋሪ በፍፁማዊ ጨዋነት እንግዳ ተቀባይ የመሆኑ ጉዳይ ነው፡፡ ይህን ያልኩት በጉዳዩ ላይ ጥናት አካሄጄ ሳይሆን፣ በየሬስቶራንቶች እና መንገዶች ላይ ካጋጠሙኝ በመነሳት በደምሳሳው የታዘብኩትን ተንተርሼ መሆኑን በትህትና እገልፃለሁ፡፡ ጓል መቀሌዎችንም፣ ‹‹የቐንየልና፣ ክብረት ይሃበልና!›› እላለሁ (ይህ ምስጋና ግን የደህንነት ሰራተኞችንም ሆነ፤ ችግር እንዳይፈጠርብን ሊጠብቀን እንደመጣ የገለፀውን የከተማዋ ፖሊስ አዛዥን አይመለከትም፡፡)
የሹክሹክታ ወሬ…
መቀሌ በከፍተኛና መካከለኛ ካድሬዎች የቅንጦት መኖሪያ ቤቶች ከመጥለቅለቋ በተጨማሪ፣ ገዥው-ፓርቲን በተራ ወቀሳም ቢሆን ስሙን ማንሳት ላልተጠበቀ የከፋ አደጋ የሚዳረግባት የአፈና መንደር መሆኗን ለመታዘብ ብዙ ድካም የሚጠይቅ አይደለም፤ በጥቂት ቀናት ቆይታዬም የታዘብኩት እውነታ አረናንና አንድነት ፓርቲን ተቀላቅለው ከሚታገሉ የከተማዋ ወጣቶች በስተቀር፣ በነዋሪው ላይ አስፈሪ ፍርሃት ማርበቡን የሚያስረግጥ ነው፡፡ በተለይም አድራሻና ማንነታቸው የማይታወቅ ‹‹ነጭ ለባሽ›› የሚል ተቀፅላ መጠሪያ ያላቸው ታጣቂዎች ‹በተቃዋሚነት የጠረጠሩትን በሙሉ አፍነው በመውሰድ ያሻቸውን ያደርጉታል› የሚል ወሬ በሹክሹክታ መዛመቱ፣ የፍርሃቱ አንድ መነሾ ሳይሆን አይቀርም ብዬ አስባለሁ፡፡ ወሬው በሕዝብ ዘንድ ይህን ያህል ስር የሰደደ ፍርሃት ማሳደር የቻለበት ምክንያት፣ ከበረሃው ዘመን ጀምሮ ‹‹ደርግን ይደግፋሉ›› ወይም ‹‹ይሰልላሉ›› ተብለው የተጠረጠሩ ነዋሪዎችን ድርጅቱ ለእንዲህ አይነት ተልዕኮ ባሰለጠናቸው አባላቱ ከመኖሪያ መንደራቸው በውድቅት ሌሊት እያፈነ ከወሰዳቸው በኋላ የደረሱበት አለመታወቁ ነው፤ ይህ ትውልድ ለፍርሃት እጅ መስጠቱም ከዚሁ ጋር እንደሚያያዝ ይነገራል፡፡ ካድሬዎቹም እንዲህ አይነት የበረሃ ወሬዎችን ሆነ ብለው እያጋነኑና እየቀባቡ በሕዝቡ መሀል ማናፈሱን ዛሬም ስለመቀጠላቸው ጥቂት የማይባሉ ወጣቶች አረጋግጠውልኛል፡፡ በአጠቃላይ በትግራይ፣ በቀድሞው የህወሓት መስራች አቶ አስገደ ገ/ስላሴ አገላለጽ ‹‹ሕዝቡ ሁሉ እስረኛ ነው››፡፡

ከአፈናዊ ማስፈራሪያዎችና ማሸማቀቂያዎች በተጨማሪ በከተማዋ ሥራ-አጥነት አለቅጥ መንሰራፋቱ እና አብዝሃው የበይ ተመልካች መሆኑ፣ የአዲሱን ትውልድ ልብ በህወሓት ላይ ካሸፈተው ውሎ ያደረ ይመስለኛል፡፡ በርግጥ ከወደ ሸገር ተጋንኖ የሚወራውን ያህል ባይሆንም፣ የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊን በመውደድ ብቻ ድርጅቱን የሚደግፉ እንደነበሩ አይካድም፤ ግና፣ ይህም ቢሆን የሰውየውን ህልፈት ተከትሎ ታሪክ ሆኗል ማለት ይቻላል፡፡ ሌላኛው የተቃዋሚውን ጎራ ያጠናከረው ምክንያት ከቀዳሚዎቹ ሁሉ የከፋ አምባገነን እንደሆነ የሚነገረው የአባይ ወልዱ ካቢኔ፣ በሙስናና መልካም አስተዳደር እጦት የሚቀርብበት ወቀሳ ነው፡፡ የእነዚህ ሁሉ ድምር ውጤት ደግሞ ‹‹ነፃ አውጪ››ውን ህወሓት እና መቀሌን ለሁለት ከፍሎ የማይተዋወቁ ዓለሞች አድርጓቸዋል ወደሚል ድምዳሜ ያደርሳል፡፡ ይህም ሆኖ ህወሓት በየትኛውም የትግራይ መሬት ተቃዋሚ ፓርቲ የመንቀሳቀስ ዕድል እንዳይኖረው ከጫካው ትግል ጀምሮ፣ በድርጅታዊ ቋንቋ ‹‹የትግራይ መሬት ከአንድ ፓርቲ በላይ መሸከም አይችልም›› የሚለውን ያልተፃፈ ሕግ ለማስፈፀም የማይፈነቅለው ድንጋይ የለም፤ ለአፈናው ቀንበር መክበድም ቀንደኛው መነሾ ይህ ነው የሚለው ጭብጥ የተጋነነ አይደለም፡፡

ከጥቂት ወራት በፊት አቦይ ስብሃት ነጋ፣ አባይ ፀሀዬ፣ ስዩም መስፍን እና ፀጋዬ በርሄ፡- መቀሌ፣ አጽብሃ ወአብርሃ፣ ውቅሮ፣ አዲግራት፣ ፈረስ ማይ፣ አድዋ፣ አክሱም፣ ሽሬ እንደስላሴ፣ አላማጣ እና ማይጨው ከተሞች ተገኝተው ከነዋሪዎቹ ጋር ስብሰባ በመቀመጥ፤ እንዲሁም ከነበለት፣ ማይቅነጣል፣ ዕዳጋ ዓርቢ፣ እንዳባጉና እና ሽራሮን ከመሳሰሉ ወረዳዎች ደግሞ የተወሰኑ ግለሰቦችን በተወካይነት ወደ መቀሌ በማስመጣት ‹‹ችግራችሁ ምንድን ነው? አለ የምትሉትን ቅሬታና የጎደለውን ነገር በሙሉ ንገሩን?›› በሚል መንፈስ የተቀኙ ጥያቄዎችን በማቅረብ ውይይት አካሄደው እንደነበር ይታወሳል፤ በዚህ ስብሰባም ሕዝቡ በርካታ ችግሮችን ከመዘርዘሩ ባለፈ፣ በአብዛኛዎቹ መድረኮች ስሜት የፈነቀላቸው አረጋውያን ሳግ እየተናነቃቸው ከሞላ ጎደል እንደሚከተለው ሊጠቃለል የሚችል ተቃውሞ መሰንዘራቸውን ሰምቻለሁ፡-

‹‹እናንተ ክዳችሁናል! ለ17 ዓመታት ልጆቻችንን በጦርነት ማግዳችሁ ስታበቁ፤ ለትግራይ ሕዝብ አንዳችም የጠቀማችሁት ነገር የለም፡፡ እንዲያውም በሌሎች ክልሎች ላይ በሚገኙ ወገኖቻችንን ላይ በምታደርሱት በደል በጠላትነት እንድንመለከት ነው ያደረጋችሁን፡፡ ከዚህ በኋላ በምንም መልኩ አናምናችሁም!!››

የቀድሞዋ የድርጅቱ የአመራር አባል አረጋሽ አዳነም ‹‹እነዚህ ሰዎች (የህወሓት መሪዎች) የምር ኢትዮጵያን ይወዳሉ ወይ? የሚል ጥያቄ ተብላላብኝ›› ማለቷን ‹‹የትግራይ ሕዝብ፣ ወያኔዎቹና ሽፍቶቹ›› መጽሐፍ ገፅ 81 ላይ መገለፁ የአዛውንቶቹን አባባል ያስረግጣል ብዬ አስባለሁ፡፡

የሆነው ሆኖ እነ አባይ ፀሀዬ ከሕዝቡ የሰበሰቡትን ቅሬታ ይዘው (በርግጥ መጀመሪያውኑም ችግሩ ስለመኖሩ ሳያውቁ ቀርተው አይደለም)፣ ከክልሉ ፕሬዚዳንት አባይ ወልዱ ጋር ተወያይተውበት ነበር፡፡ ፕሬዚዳንት አባይም በድርጅታዊ መዋቅር የቀድሞ አለቆቹ እቢሮው ተገኝተው አንድ በአንድ የዘረዘሩለትን ችግር ካደመጠ በኋላ እንዲህ ሲል መለሰላቸው፡- ‹‹እናንተ ያነጋገራችሁት ተቃዋሚ-ተቃዋሚውን ብቻ እየመረጣችሁ ነው፤ የመጣችሁትም ልክ እንደ ተቃዋሚዎች እንከን ፍለጋ ነው››፡፡

መቼም ከዚህ የበለጠ አስገራሚ የፖለቲካ ቀልድ ያለ አይመስለኝም፡፡ ምክንያቱም ይህ ነገር ሄዶ ሄዶ አንድምታው ‹‹ህወሓት እኛ እንጂ እናንተ አይደላችሁም›› የሚል የልዩነት መልዕክት ይኖረዋልና ነው፡፡ ይህ ደግሞ በመለስ ህልፈት ማግስት ‹‹የአዲስ አበባው›› እና ‹‹የመቀሌው›› ተብሎ ለሁለት መከፈሉ ሲነገር የነበረው የህወሓት የውስጥ መተጋገል ገና መቋጫ ላለማግኘቱ አመላካች ተደርጎ ሊወሰድ ይችላል (በነገራችን ላይ እነ አባይ ፀሀዬ በብዙ ሺህ ቅጂዎች የታተመ መጠይቅ በተለያዩ የትግራይ አካባቢዎች በትነው የነበረ ሲሆን፤ በቅርቡ ደግሞ የተሞላው መጠይቅ ተሰብስቦ ወደ አዲስ አበባ መላኩን ሰምቻለሁ፡፡ ይሁንና ውጤቱ ምንም ይሁን ምን አዲስ ነገር ይኖራል ብዬ ግን አላስብም፤ ምክንያቱም ከአስራ ሶስት ዓመት በፊት በዋነኛ መሪዎቿ አንደበት ‹‹ህወሓት ከአናቷ በስብሳለች›› ተብሎ ከተመሰከረባት ክፉ ህመሟ አለመፈወሷ ዛሬም በገሀድ ይታያልና)
የትግራይ እጣ-ፈንታ
በአስከፊው የትጥቅ ትግል ያለፈው የአካባቢው ነዋሪ፣ በህወሓት ላይ የነበረው ተስፋ መሟጠጡን የሚያስረግጥልን፣ ከላይ ያየነው የመቀሌ ገፅታ እና በተለያዩ የክልሉ ከተሞች ያሉ ነዋሪዎች ለጉምቱ የድርጅቱ ታጋዮች ያቀረቡት ብሶት ብቻ አይደለም፤ አርሶ አደሩም በበርካታ ችግሮች ተተብትቦ በስቃይና በድህነት ኑሮውን የመግፋቱ ጉዳይ ጭምር እንጂ፡፡ በተለይም መሬትና ማዳበሪያ ወሳኝ የፖለቲካ ካርድ ሆነዋል፡፡ ማዳበሪያው በክልሉ በጀት የሚገዛ ቢሆንም፣ በዱቤ የማከፋፈሉን ስራ የሚያሳልጠው ደደቢት ብድርና ቁጠባ ነው፡፡ ብዙሃኑ አርሶ አደርም ከዚህ ተቋም በዱቤ የገዛውን ማዳበሪያ መክፈል ባለመቻሉ በዕዳ የመያዝ ክፉ ዕጣ-ፈንታ ይገጥመዋል፡፡ ስለዚህም ያለው አማራጭ ሁለት ብቻ ይሆናል ማለት ነው፡፡ የመጀመሪያው ሚስቱንና ልጆቹን አዲስ አበባን ጨምሮ በተለያዩ ከተሞች ለልመና አሰማርቶ በሚያገኘው ገንዘብ እንደምንም ዕዳውን ከፍሎ፣ የፈለገውን የፖለቲካ አመለካከት መያዝ የሚችልበትን አጋጣሚ ማመቻቸት፤ ወይም ከህወሓት ጎን በመቆም ዕዳው ተሰርዞለት፣ የሴፍቲኔት ተጠቃሚም ሆኖ በጭቆና አገዛዝ ውስጥ ማዝገም ነው፡፡ ላለፉት ሃያ ሶስት ዓመታትም የሰሜን ኢትዮጵያ መልከዓ-ምድር ይህን በመሰለ ፍርሃትና በአንድ ርዕዮተ-ዓለም ተጠርንፎ ማደሩን ማን ይክደው ይሆን?
የመጪው ጊዜያት የብቻ ፍርሃት…
በዚህ አውድ የማነሳው የትግራውያን ከባድ ፍርሃት፣ ከክፉው የህወሓት አስተዳደር ጋር የሚያያዝ ነው፡፡ በሀገሪቱ በነቢብ ገዥ-ፓርቲ ተደርጎ የሚታሰበው ኢህአዴግ መሆኑ ባይስተባበልም፣ ግንባሩን የፈጠሩት አራቱ ድርጅቶች በፖለቲካዊ ተፅእኖም ሆነ በአንዳንድ መንግስታዊ ቁልፍ ኃላፊነቶች ላይ እኩል ውክልና ያሌላቸው መሆኑ አያከራክርም፤ ይህንን ያፈጠጠ ሀቅ አምኖ አለመቀበሉም መፍትሔውን ሊያርቀው እንደሚችል መዘንጋት የለብንም፡፡ ለማሳያም እንደ ኢህአዴግ ባለ አምባ-ገነን አገዛዝ ውስጥ ከምንም በላይ ወሳኝ የሆኑት የደህንነት እና የመከላከያ ሠራዊቱ አወቃቀር በህወሓት የበላይነት መሆኑን መጥቀስ ይቻላል፡፡ በአንድ ወቅት አቶ መለስ ዜናዊም በመከላከያ ውስጥ ያለውን ፍትሓዊ ያልሆነ ውክልና ከማመኑም በዘለለ፣ በበረሃው ዘመን ታጋዩ በአብላጫው የህወሓት አባል የነበረ መሆኑን እንደ ምክንያት ማቅረቡ ይታወሳል፡፡ በአናቱም ድርጅቱ በመሀል ሀገር ያጣውን ድጋፍ ለማካካስ፣ ራሱን የትግራይ ብሔረተኛ አስመስሎ ከማቅረቡም ባለፈ፣ እንዲህ አይነት ከፋፋይ መንፈሶች እንዲናኙ በርትቶ ለመስራቱ በርካታ ማስረጃዎች አሉ፤ ‹‹እኛ ከሌለን የትግራይ ህዝብ ለአደጋ ይጋለጣል›› ከሚለው አፍራሽ ቅስቀሳው አልፎ፣ በ97ቱ ምርጫ ወቅት የኢንተርሃሞይ ጨዋታን ወደ ክርክሩ መድረክ ያመጣበትን አውድ እና በ2002ቱ ምርጫ አንድነትን ወክሎ በተምቤን ለመወዳደር የቀረበውን አቶ ስዬ አብርሃንም ሆነ አረና ፓርቲን ለማጥላላት የተጠቀመበትን ፖለቲካ መጥቀሱ ብቻ በቂ ነው፡፡ በቅርቡ የሙስሊሙ መንፈሳዊ መሪዎችም ምርምራ የተደረገባቸውም ሆነ ስቅየት የደረሰባቸው በአንድ ቋንቋ ተናጋሪ መርማሪዎች መሆኑን ለፍርድ ቤት መናገራቸው ተጨማሪ ማሳያ ነው፤ መቼም የማዕከላዊ ምርመራ ኃላፊዎች፣ ከሌሎች ብሔሮች የተገኙ መርማሪዎችም ሆነ ጨካኝ ገራፊ የፖሊስ አባላት አጥተው አይመስለኝም፤ እንዲህ አይነት አመለካከት በሕዝብ ዘንድ እንዲሰርፅ የሚሹ ፖለቲከኞችን ትዕዛዝ ማስፈፀም እንዲቻል እንጂ፡፡ ይህ እውነታም በአንዳንድ ቦታዎች ድርጅትንና ሕዝብን ቀላቅሎ ለጅምላ ፍረጃ ማጋለጡ አሌ አይባልም፡፡ እነዚህ ሁኔታዎች ደግሞ በክልሉ ላይ ብሔራዊ ሥጋት ፈጥረው ሕዝቡን አማራጭ አልባ አድርገው ድርጅቱን እንደጋሻ እንዲመለከት ቢያስገድዱ አስገራሚ አይሆንም፡፡
ሳልሳዊ ወያኔ
በብላታ ኃይለማርያም ረዳ ፊት-አውራሪነት በ1935 ዓ/ም ትግራይን በአፄው ላይ እንድታምፅ ያነቃቃው የወያኔነት እንቅስቃሴ፤ በያኔዋ የአፄው የክፉ ቀን ወዳጅ ታላቁ ብሪታኒያ ማበር ጭምር ሲቀለበስ፤ በክሽፈቱ ፅንስ ውስጥ ሌላ ትውልድ እንደሚገነግን ግልፅ ነበር፡፡ እናም የእነ ኃይለማርያምን ኢትዮጵያዊነት ጨፍልቀው የተነሱት እነ ስብሐት ነጋ፣ ያን ብርቱ የማህበረሰብ ክፍል ሰቆቃ ጠምዝዘው ከማህበረ-ባህሉ የተጣረሰ መንገድ መርጠው ሸገር ሲደርሱ፤ እነርሱኑ ካፈራ መሬት፣ የተቀለበሰውን ዳግማይ ወያኔ ረግጦ የሚነሳ ትውልድ እንደሚመጣ ዘንግተው ሰንብተዋል፡፡ ይሁንና ከላይ በመግቢያዬ የጠቀስኩትን የወልቃይቱን ትምህርት ቤት ኩነት በወቅቱ በቦታው የነበረው መምህር ሀጎስ አርዓያ (ስሙ የተቀየረ) እንደተረከልኝ፣ ራሳቸውን የትግራይ ህዝብ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ/ትህዴን/ ብለው በሚጠሩ ነፍጥ-አንጋች ፋኖዎች የተፈፀመ የመሆኑ እውነታ የህወሓትን የተሳሳተ ግምት ያስረግጣል ብዬ አምናለሁ፡፡ ይህ የሳልሳዊ ወያኔ ወኪል እንደሆነ እየታመነ የመጣ የሚመስለው ስብስብ ሁመራ፣ ወልቃይትና ሽሬን በመሳሰሉ ከባቢዎች እንዳሻው የመንቀሳቀስ አቅም መገንባቱ ይነገራል፡፡ ድርጅቱ ከአስራ ሶስት አመት በፊት ወደ ኤርትራ በተሰደደው የህወሓት ሰው ፍሰሀ ኃይለማርያም ተድላ አስተባባሪነት መመስረቱ ይታወሳል፡፡ እንደ ትህዴን እምነት መሪው ፍስሀ ከስድስት ዓመት በፊት በኢትዮጵያ መንግስት ደህንነቶች ነው የተገደለው፤ ከዚያን ጊዜም ወዲህ ሌላኛው የህወሓት አባል የነበረው ፀጋዬ ሞላ አስገዶም ከግማሽ መቶ ሺ አያንስም የሚባለውን ታጣቂ እንቅስቃሴ እየመራ እንደሆነ ንቅናቄውን በተመለከተ የሚወጡ መረጃዎች ያሳያሉ፡፡ ድርጅቱ ለፕሮፓጋንዳ ሥራው የራሱ ቴሌቪዥንና ራዲዮ፤ እንዲሁም ‹‹መጽሔተ ብስራት›› የተሰኘች በአማርኛና ትግርኛ የምትዘጋጅ የህትመት ውጤት እንዳለው ይታወቃል፡፡
ትህዴን የመረጠው የትግል ስልት ትክክል ነው አይደለም የሚለውን ሙግት ወደጎን ትተን፣ ኢትዮጵያን የሚመለከትበት መንገድ አስደማሚ ነው፡፡ በ1993 ዓ.ም አጋማሽ በለቀቀው የፖለቲካ ፕሮግራሙ ላይ እንደገለጸው፣ ዓላማው ‹‹አንዲት ዴሞክራሲያዊት ኢትዮጵያን መገንባት ነው››፤ የንቅናቄው ጠንከር ያለ የክልሉን የድጋፍ መሰረት ስናስተውል፣ የአንዲት ኢትዮጵያ መንፈስ የትግራዋይ ዋነኛው መለዮ መሆኑን ያስረግጥልናል፡፡ ‹ትግራይ የኢትዮጵያ መፈጠሪያ መሬት ናት› የሚለው የስብስቡ ድምፅ፣ ‹‹ትላንት የተፈጠረች›› ከሚለን ህወሓት ጋር ያለውን ተፃርሮሽ ፍንትው አድርጎ ያሳየናል፡፡ ፕ/ር መሳይ ከበደም፣ ከሳምንት በፊት በበተኗት መጣጥፍ ለድርጅቱ ቡራኬያቸውን እንዲሰጡት ያስገደዳቸው፣ ይኸው የአንዲት ኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊነት ምስረታ ናፍቆት ይመስለኛል፡፡ አንቀፅ 39፣ ኢትዮጵያውያን እንዲበታተኑ የሚያደርግ በከፋፍለህ ግዛ የመገንጠል ፖሊሲ የተቀኘ እንደሆነ የሚከራከረው ንቅናቄው፣ ‹‹የትግራይ ሕዝብ በኢትዮጵያ ሉአላዊነት የሚያምን ነው›› ሲል ህወሓት የማያውቃትን ትግራይ ይነግረናል፡፡ መሪው ፀጋዬ ሞላም ‹‹የትህዴን አላማ የትግራይ ሕዝብ ጥያቄን ብቻ ሳይሆን የኢትዮጵያን ሕዝብ ጥያቄም ለመመለስ እንደሚታገል›› አበክሮ ይሟገታል፡፡ የሆነው ሆኖ የ17ቱ ዓመታት መራር የትጥቅ ትግል ዋና ገፈት ቀማሽ በሆነች ምድር፣ ዛሬም በተመሳሳይ መንገድ የሥርዓት ለውጥ ለማምጣት በሺዎች የሚቆጠሩ ነዋሪዎቿ ‹‹ዱር ቤቴ!›› ማለታቸው ስለህወሓት ክሽፈት ‹‹ግዛቴ›› በሚለው መሬት በግላጭ መታወጅን ይመሰክራል፡፡

በመጨረሻም የለውጡ መንፈስ በመላ ሀገሪቱ እንዲናኝ ከትህዴን የጠቀስኳቸው መሰል መንፈሶች ጋር የሚስማማ አረዳድ ያለው አረና እና በስሩ የተሰባሰቡት ወጣቶችም ሆኑ የብሔሩ ልሂቃን፣ የትግራይን የመከራ መስቀል የሌላ ቋንቋ ተናጋሪ ግፉዓንም እንዲጋሩ የማሳመን ሥራ ይጠበቅባቸዋል፡፡ በርግጥ ይህን መሰል የተንሸዋረረ አረዳድ ለመኖሩ ዋነኛው መነሾን ትህዴን በፖለቲካ ፕሮግራሙ እንዲህ ሲል መግለፁ መዘንጋት የለበትም፡-

‹‹ከሁሉም በላይ የሚያሳዝነው ደግሞ ወያኔ (ማሌሊት) ለትግራይ ሕዝብ ብቸኛ ጠበቃ መስሎ በመቅረብ በሌሎች ሕዝቦች ላይ እየፈፀማቸው ባሉ ግልፅና ስውር ወንጀሎች ሳቢያ የትግራይ ሕዝብ በገዛ አገሩ በአይነ-ቁራኛና በጥርጣሬ እንዲታይ ማድረጉ ነው፡፡››

ያለፈው አልፏል፤ በመጪው ጊዜያት ይህን ፍርሃት አሸንፎ ትግርኛ ተናጋሪውን ኢትዮጵያዊ የለውጡ አካል ለማድረግ፣ ለሥርዓት ቅየራው የሚካሄደው ትግል ዘርን መሰረት ያደረገ አግላይ የመከራ መስቀልን በጋራ ለመሸከም ዝግጁ መሆንን የሚያካትት ሊሆን ይገባል ብዬ አስባለሁ፡፡ ምክንያቱም ጠረጴዛው ላይ ያለው ምርጫ ሁለት ብቻ ነውና፤ ወይ አብሮ መውደቅ፣ አልያም በህብረት መነሳት፡፡ እስከዚያው እነ አባይ ፀሐዬን ከደርግ የሰማይ እሩምታ የከለሉ የትግራይ ተራሮች፣ ለትህዴን ጓዶችም እንደማይጨክኑ በመተማመን እናዘግማለን፡፡


የደ/ሰ/መ/ቤ/ክ ፓሪሽ ፕሮግራም አመታዊ ሄልዝፌር (በሚኒሶታ ለምትኖሩ ወገኖቻችን ነፃ የህክምና ምርመራና ትምህርት ቀን)

$
0
0

Posterhealthfair2014 (1)

የ ደ/ሰ/መ/ቤ/ክ ፓሪሽ ፕሮገራም አመታዊ ሄልዝፌር
ዋናውን ድጋፍ ሰጪ፡ Ucare
በእለቱ የሚሰጡ አገልግሎቶች፤
1) የደም ግፊት፡ስኳር፤ከለሰትሮል፤ክብደትን መለካት፡
2)የጤና መረጃ መስጠት፤በተለይም በልብ/ደምስር ጋር የተያያዙ፤በሽታዎችን፡ኢንፌክሽን፤ የአእምሮ ጤንነትን እነዲሁም የጤና መድህን በተመለከት
3)በእዚሁ እለት ሐኪሞች በቦታው በመገኘት ጠቃሚ ምክር እና መረጃ ይሰጣሉ፤፤
በእለቱ አገልግሎቱን ከሚሰጡ ግለሰቦች/ድርጅቶች፡ የ.ደ.ሰ.መ.ቤ.ክ ጤና ክፍል፤
በሚኒያፕለስ እና አካባቢ የሚኖሩ የጤና ባለሙያዎች( ኢትዮጲያዊያን እንዲሁም ሌሎች) ፤U of MN-Fairview ይገኙበታል፤፤
ቦታ፡4401 DSMA 4401 Minehaha Avenue Minneapolis MN 55406
ሰአቱ፡ ከቅዳሤ በኋላ 10AM
የሰው ልጅ ጤነኛ ሆኖ በህይወት ለመኖር የእግዚአብሔርን ህግ በመከተል በመጠን መኖር እንደሚገባ መፅሐፍ ቅዱስ በሰፊው ያስተምራል፡፡

አዲስ ዜና –ሰላማዊ ትግል 101 መጽሐፍ በግርማ ሞገስ

$
0
0

በአይነቱ የመጀመሪያ የሆነው እና ሰላማዊ ትግል 101 በሚል ስያሜ የሚጠራው አዲስ መጽሐፍ በኢትዮጵያ ገበያ ላይ ውሏል። ሰላማዊትግል 101 የተዘጋጀውበሰላማዊትግልየኢትዮጵያን ህዝብ የመንግስት እና የአገሩ ባለቤት በማድረግ ኢትዮጵያን ወደ ዴሞክራሲመውሰድየሚሹአገርወዳድኢትዮጵያውያንበተለይም ወጣቱ ኢትዮጵያዊ የሆነ ትምህርታዊየመወያያመጽሐፍእንዲኖረውታቅዶ ነው።ስለዚህ ሰላማዊ ትግል 101 በአቀራረቡም ሆነ በይዘቱ የውጭ አገር ቅጅ ሳይሆን ኢትዮጵያዊ ነው።

ሰላማዊትግል 101 ከአልበርትአነስታይንሰላማዊትግልምርምር ተቋምዘመናዊስራዎችውስጥ ጠቃሚዎቹን አቅልሎ አቅርቧል። መጽሐፉ የመንግስት ስልጣን ባለቤት ህዝብ ነው የሚለው አባባል መሰረቱ  የፖለቲካ ኃይል ምንጮች ባለቤትነቱ መሆኑን፣ የፖለቲካ ኃይል ድጋፍ ምሶሶዎች ሚና ምን እንደሆነ፣ የሲቪክ ድርጅቶች ሚና፣ ሴቶች ለሰላማዊ ትግል ያላቸው ተፈጥሮዋዊ ቅርበት፣ የሰላማዊ ትግል መፈጸሚያ መሳሪያዎች እነማን እንደሆኑ፣  ሰላማዊ ትግል ህዝብን እንዴት የራሱ ነፃ አውጭ እንደሚያደርገው እና የመሳሰሉትን የሰላም ትግል መሰረታዊ ጽንሰ አሳቦች አቅልሎ ይተነትናል።

መጽሐፉ ስለሰላማዊትግልእድገትታሪክይተርካል። ይህን ሲያደርግ ግን ከክርስቶስ ልደት ቀደም ብሎ ጀምሮ የሰው ልጅ በየክፍለ ዘመኑ በፍልስፍና እና በንድፈ አሳብ ደረጃ ካደረገው እድገት ጎን ለጎን የየዘመኑን ታሪካችንን በትይዩ በማመላከት አንባቢን ንፅፅራዊ ግንዛቤ ለማስጨበጥም ይሞክራል።

በኃይልየሚፈጸመውየመንግስትሽግግርባህላችንመለወጥ እንዳለበትለማስረዳትሰላማዊትግል 101 ከአክሱም ዘመን አንስቶ እስከ ዛሬ ድረስ በተደረጉ የመንግስት ሽግግሮች የሆነውን፣ የተደረገውን እና የተፈጸመውን አሳዛኝ ታሪካችንን በአጭሩ ይተርካል። ሰላማዊትግል 101 ዴሞክራሲ በዳበረበት በምዕራቡ አለም እና አምባገነኖች በሚገዟቸው አገሮች ስለሚደረገው ምርጫልዩነት ዘርዘርአድርጎ አቅርቧል።የአሜሪካን፣የግብጽን፣የሰርቢያንናየዝምባቡዌንሰላማዊትግልናምርጫልምዶችምበየምዕራፉተንትኗል።ከኃይለስላሴዘመነመንግስትጀምሮለ80 አመታትያህልበኢትዮጵያየተደረጉትንምርጫዎችምይገመግማል ሰላማዊ ትግል 101።

ሰላማዊ ትግል 101 መጽሐፍ 232 ገጾች አሉት። ከፍ ብለው ከተጠቀሱት ቁም ነገሮች በተጨማሪ ብዙ ጠቃሚ ነገሮችን ይዞ በኢትዮጵያ ገበያ ላይ ቀርቧል። በቅርቡ ደግሞ በሰሜን አሜሪካ፣ በአውሮፓ እና በአውስትራሊያ ገበያዎች ይቀርባል። መልካም ንባብ። መልካም ውይይት።
bk

መድረክ በሐዋሳ የጠራው ሰላማዊ ሠልፍ በእንግልት ተካሄደ

$
0
0

61

የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ መድረክ (መድረክ) እና አባል ድርጅቶቹ የሲዳማ አርነት ንቅናቄ (ሲአን)፣ የኢትዮጵያ ማኅበረ ዲሞክራሲ ደቡብ ኅብረት አንድነት ፓርቲ

(አማዲደህአፓ)፣ የኦሮሞ ፌዴራሊስት ኮንግረስ (ኦፌኮ) እና አረና ትግራይ ለዲሞክራሲና ሉዓላዊነት ፓርቲ (አረና) ጋር በደቡብ ክልል ዋና ከተማ ሐዋሳ ያካሄደው ሰላማዊ ሠልፍ በእንግልት መካሄዱን አስታወቀ፡፡ 

የአገሪቱን ወቅታዊ ሁኔታ አስመልክቶ ‹‹ሰላማዊና ዲሞክራሲያዊ ተቃውሞዎችን በኃይል ማፈን ይቁም›› በሚል ሰኔ 7 ቀን 2006 ዓ.ም. በሐዋሳ ከተማ ያካሄደው ሰላማዊ ሠልፍ በሰላም ቢጠናቀቅም፣ ገዥው ፓርቲ ሕዝቡ ወደ ሠልፍ እንዳይወጣ የተለያዩ ማነቆዎችን መፍጠሩን መድረክ ገልጿል፡፡ የፓርቲው ሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ጥላሁን እንደሻው፣ ‹‹ገዥው ፓርቲ አፈና ሲያደርግብን ነበር፡፡ ቅዳሜ ልናካሄድ ላሰብነው ሰላማዊ ሠልፍ የዕውቅና ደብዳቤ የሰጠን ሐሙስ 11 ሰዓት ላይ ነው፤›› በማለት ገዥው ፓርቲን የኮነኑ ሲሆን፣ ‹‹ቢሆንም ግን ሕዝቡ ይህን አፈና ተቋቁሞ በመውጣት የተሳካ ሠልፍ አካሂደናል፤›› ሲሉ ለሪፖርተር አስረድተዋል፡፡   

ፓርቲው አገሪቱ ውስጥ ተፈጥረዋል ያላቸውን መሠረታዊ ችግሮች በዝርዝር ለሕዝብ ያቀረበ መሆኑን፣ በሕገ መንግሥቱ ተደንግገው ነገር ግን መፈጸም ያልተቻሉ ያላቸውን ዝርዝር ጉዳዮች እንዲሁ ለሕዝቡ ማቅረቡን ገልጿል፡፡ 

መሠረታዊ ችግሮች በሚል ፓርቲው በዝርዝር ካስቀመጣቸው ነጥቦች መካከል የሕዝቡ የሥልጣን ባለቤትነት እውን እንዳይሆንና የመድበለ ፓርቲ ዲሞክራሲ በትክክል ሥራ ላይ እንዳይውል የምርጫ ቦርድ ለኢሕአዴግ ወገንተኛ መሆኑን፣ በነፃነት በሰላማዊ መንገድ ለመንቀሳቀስ በሚፈልጉ ተቃዋሚ ፓርቲዎች ላይ ልዩ ልዩ የማቀጨጭ ሥልቶችን ተጠቅሞ ተፅዕኖዎችን ማድረጉን፣ በብልሹ አስተዳደርና በከፋፍለህ ግዛ ሥልቱ በተለያዩ ብሔር ብሔረሰቦች መካከል በተለያዩ ክልሎች በርካታ ግጭቶች ተፈጥረው የብዙ ዜጐች ሕይወትና ንብረት መውደሙን፣ ሐሳብን በነፃነት የመግለጽ መብታቸውን በመጠቀም በጽሑፍ፣ በንግግርና በሰላማዊ ሠልፍ ለመግለጽና ኢፍትሐዊና ኢሕገ መንግሥታዊ በሆነው አገዛዝ ላይ ተቃውሞዎችን ለማሰማት ጥረት የሚያደርጉ ዜጐችን ለእስራትና ለተለያዩ ሥቃዮች መዳረጉን፣ ዜጐች ሕገ መንግሥታዊ መብታቸውን በአግባቡ እንዳይጠቀሙ ማድረጉንና በመንግሥት ቁጥጥር ሥር የሚገኙ መሠረታዊ የሆኑ የሕዝብ አገልግሎቶች ማለትም ኤሌክትሪክ፣ ውኃ፣ ስልክና የመሳሰሉት አገልግሎቶች ኃላፊነት በጐደለው አሠራር አቅርቦታቸው እየተዛባ ሕዝቡ ለተለያዩ ችግሮች መዳረጉንና ማማረሩን መድረክ ጠቃቅሷል፡፡

ከዚህ በተጨማሪም ፓርቲው ለዘረዘራቸው ችግሮች መፍትሔ ያላቸውን ሐሳቦች ያቀረበ መሆኑን፣ ከእነዚህም ውስጥ ለትክክለኛ የመድበለ ፓርቲና ዲሞክራሲ ሥርዓት ግንባታ ተግባራዊነት፣ ለተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲዎች ነፃና ሕጋዊ እንቅስቃሴዎችና ነፃ የውድድር ሁኔታዎችን ማመቻቸት፣ በዜጐች መካከል የሚደረግ የፖለቲካዊ ወገንተኝነት አሠራር እንዲቆምና ፍትሐዊና እኩልነት የሰፈነበት አስተዳደር እንዲኖር ማድረግ፣ ዓለም አቀፍ ደረጃን የጠበቀና የፓርቲዎችን ግንኙነት ብቻ ሳይሆን ገለልተኛ የምርጫ ቦርድና ገለልተኛ የምርጫ ታዛቢዎችን ያካተተ የምርጫ ሥነ ምግባር ደንብ እንዲኖርና በትክክል ተግባራዊ ማድረግና ለፖለቲካ ፓርቲዎች የመንግሥትን የድጋፍ ገንዘብ በእኩልነትና ፍትሐዊ በሆነ መንገድ እንዲያገኙ ማድረግ የሚሉት ይጠቀሳሉ፡፡ 

ይህ በሐዋሳ የተካሄደው ሠልፍ አዲስ አበባ ላይ ተደርጐ ከነበረው ሠልፍ ጋር ተመሳሳይ ዓላማ እንዳለው የገለጹት አቶ ጥላሁን፣ በቀጣይም በሌሎች ከተሞች ተመሳሳይ ዓላማ ያላቸው ሠልፎች እንደሚካሄዱም አክለው ገልጸዋል፡፡        

Source: Ethiopian Reporter     

አንድነትና መኢአድ የውህደት ጥያቄያቸውን ለምርጫ ቦርድ አቀረቡ

$
0
0

61c

የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ) እና አንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ (አንድነት) ለረጅም ጊዜ ሲያካሂዱት የነበረውን ድርድራቸውን አጠናቀው የቅድመ

ውህደት ስምምነት በቅርቡ ካደረጉ በኋላ፣ በመጪው ሐምሌ 5 እና 6 ቀን 2006 ዓ.ም. በሚያካሂዱት ጠቅላላ ጉባዔ ለመዋሀድ እየሠሩ መሆናቸውን የመኢአድ ፕሬዚዳንት አቶ አበባው መሐሪ አስታወቁ፡፡ ምንም እንኳን ሐምሌ 5 እና 6 የሚለው በጊዜያዊነት የተያዘ ቢሆንም፣ በዚህ ጊዜ ለመዋሀድ ለምርጫ ቦርድ ጥያቄ ማቅረባቸውን አስረድተዋል፡፡

ቅድመ ውህደት ስምምነቱን ተከትሎ ከሁለቱም ፓርቲዎች የተውጣጡ አሥር አባላት ያሉት ኮሚቴ በመምረጥ የውህደት ሥራው እየተሠራ እንደሚገኝ ጠቁመው፣ ‹‹ይህም ሥራ ያለምንም እንከን በመካሄድ ላይ ነው፤›› ብለዋል፡፡

በአገር ውስጥም ሆነ በመላው ዓለም የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ጉዳዩን በቅርበት እየተከታተሉትና ውህደቱን በጉጉት እየጠበቁት እንደሆነ የገለጹት አቶ አበባው፣ ውህደቱም በተያዘለት ጊዜ እንደሚከናወን ያላቸውን እምነት አስረድተዋል፡፡

በጊዜያዊነት ከተያዘው ቀን በፊት ሁለቱም ፓርቲዎች ባቋቋሙት ኮሚቴ አማካይነት የውህደቱ ስብሰባ የት እንደሚካሄድ እንዲሁም የፋይናንስና ተያያዥ ጉዳዮችን በሚመለከት እየሠሩ እንደሚቆዩም አክለው አብራርተዋል፡፡

በውህደት የሚፈጠረው ፓርቲ አዲስ ስያሜ ስለሚኖረው ሁለቱም ፓርቲዎች የየራሳቸውን አንድ አንድ ስያሜ በማቅረብ ከውህደቱ በፊት በውይይት እንደሚፀድቅና አዲስ ዓርማም እንደሚኖረው ጠቁመው የተቋቋመው ኮሚቴም እነዚህን ሥራዎች እየሠራ እንደሚቆይም አቶ አበባው አስረድተዋል፡፡

Source: Ethiopian Reporter

ጋዜጠኞቹና ጦማሪያኑ ያለምንም ማስረጃ መታሰራቸውን የፖሊስ የምርመራ ሒደት እንደሚያሳይ ጠበቃቸው አሳወቁ

$
0
0

ፖሊስ በየቀጠሮው የሚያነሳቸው የምርመራ ምክንያቶች በፍርድ ቤት ታገዱ

በሽብርተኝነት ተጠርጥረው በእስር ላይ የሚገኙት ጋዜጠኞችና ጦማሪያን ያለምንም ማስረጃ መያዛቸውን፣ ፖሊስ ለአራት ጊዜ ፍርድ ቤት በመቅረብ ለችሎት ከሚያስረዳው የምርመራ ሒደት መረዳት መቻሉን ጠበቃቸው አስታወቁ፡፡

zone9-e1398747809895የተጠርጣሪዎቹ ጠበቃ አቶ አመሐ መኰንን ይህንን የተናገሩት ሰኔ 7 ቀን 2006 ዓ.ም. ለአራተኛ ጊዜ በፌዴራል የመጀመርያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ ወንጀል ችሎት ቀርበው በነበሩት ጋዜጠኞች ተስፋለም ወልደየስ፣ አስማማው ኃይለ ጊዮርጊስ፣ ኤዶም ካሳዬ፣ ጦማሪያንና መምህር ዘለዓለም ክብረት፣ አጥናፍ ብርሃኔና ናትናኤል ፈለቀ ላይ ፖሊስ ለፍርድ ቤቱ ቀድሞ በተፈቀደለት 28 ቀናት ውስጥ ‹‹ሠርቻለሁ›› ያለውን የምርመራ ሒደት ተከትሎ ነው፡፡

ተጠርጣሪዎቹ በቁጥጥር ሥር ውለው በፌደራል ወንጀል ምርመራ ማዕከል (ማዕከላዊ) በእስር ላይ በቆዩባቸው 50 ቀናት ውስጥ አራት ጊዜ ፍርድ ቤት ሲቀርቡ፣ በአንድ ቀጠሮ የተጠርጣሪዎቹ ቤተሰቦች የሆኑ ብቻ ሁለት ሁለት ሰዎች ችሎቱን እንዲታደሙ የተደረገ ቢሆንም፣ ሰኔ 7 ቀን 2006 ዓ.ም. ግን ማንም ሰው ወደ ችሎት እንዳይገባ ተከልክሏል፡፡ በመሆኑም ተጠርጣሪዎቹ የፍርድ ቤት ውሎአቸውን ጨርሰው ሲወጡ ጠበቃቸውን አቶ አመሐን የአገር ውስጥና የውጭ መገናኛ ብዙኃን፣ እንዲሁም ከቤተሰብ ጀምሮ ዲፕሎማቶች፣ ጓደኞቻቸውና ሌሎች በፍርድ ቤቱ ቅጥር ግቢ ውስጥ የተገኙ ታዳሚዎች ከበቧቸው፡፡

‹‹ምን ተባሉ? ፖሊስ ምን ተጨማሪ ምርመራ አቀረበ?›› ለሚለው የሁሉም ታዳሚዎች ጥያቄ ምላሽ መስጠት የጀመሩት ጠበቃ አመሐ፣ ‹‹ፖሊስ አዲስ ነገር አላቀረበም፤›› ካሉ በኋላ፣ ባለፉት 28 ቀናት ውስጥ ምን ምን ሥራዎችን እንደሠራ ፍርድ ቤቱ ጠይቆት የተወሰኑ የትርጉም ሥራዎችን እንዳሠራ፣ የተወሰኑ የባንክ ማስረጃዎችን እንዳገኘ፣ የተወሰኑ የቴክኒክና ሌሎች በርካታ ሥራዎችን መሥራቱን እንዳስረዳ ገልጸዋል፡፡ በርካታ ሥራዎች የሠራ ቢሆንም ከሥራው ውስብስብነትና ስፋት አንፃር በርካታ ሥራዎች እንደሚቀሩት በመግለጽ፣ ለተጨማሪ ምርመራ 28 ቀናት እንዲፈቀድለት ፍርድ ቤቱን መጠየቁን አቶ አመሐ ተናግረዋል፡፡

መርማሪ ፖሊስ ‹‹በርካታ ሥራዎች›› በማለት በጥቅል የተናገረውን በሚመለከት የሠራውንና ያልሠራውን አንድ ሁለት ብሎ እንዲያስረዳ ፍርድ ቤቱ እንዳዘዘው የገለጹት ጠበቃው፣ የተወሰኑትን የምስክሮች ቃል ተቀብሎ የተወሰኑትን መቀበል እንደሚቀረው፣ ተባባሪዎች ወደ ክልል በመሄዳቸው የምርመራ አባላትን ልኮ እየተጠባበቀ መሆኑን፣ አዲስ አበባ ውስጥም ያልያዛቸው ተባባሪዎች እንዳሉና ለመያዝ እየሠራ መሆኑን፣ የተወሰነ ሰነድ ማስተርጐም እንደሚቀረው አስረድቶ የጠየቀው ጊዜ እንዲፈቀድለት በድጋሚ መጠየቁን አስረድተዋል፡፡

ጠበቃ አመሐ በበኩላቸው፣ መርማሪ ፖሊሶቹ ያቀረቡትን ሪፖርት በመቃወም መከራከራቸውን ተናግረዋል፡፡ ተጠርጣሪ ደንበኞቻቸው ከታሰሩ 50 ቀናት እንዳለፋቸው፣ አራት ጊዜ ፍርድ ቤት ቀርበው ጊዜ ቀጠሮ ተጠይቆባቸው እንደተፈቀደ፣ የፈለገ ውስብስብ ወንጀል ቢሆን እንኳን ከተያዙ ጊዜ ጀምሮ ምርመራ ቢጀመር 50 ቀናት ምርመራ ለማጠናቀቅ በቂ መሆኑን ለፍርድ ቤቱ ማስረዳታቸውን ገልጸዋል፡፡

‹‹ይኼ የሚያሳየው ፖሊስ ተጠርጣሪዎቹን የያዛቸው ምንም ዓይነት ማስረጃ ሳይኖረው መሆኑን ነው፤›› ያሉት ጠበቃ አመሐ፣ ተጠርጣሪዎቹን ዋጋ እያስከፈላቸውና ሕግን የጣሰ ተግባር በመሆኑ የመርማሪ ፖሊስን የምርመራ ውጤት ፍርድ ቤቱ ሊቀበለው እንደማይገባ በመናገር መከራከራቸውን አብራርተዋል፡፡

መርማሪ ፖሊስ በተደጋጋሚ ለፍርድ ቤት የሚያነሳቸው የምርመራ ሒደቶች ማለትም ትርጉም ማስተርጐም በተርጓሚውና በፖሊስ መካከል የሚከናወን መሆኑን፣ የቴክኒክ ምርመራውም በራሱ በፌዴራል ፖሊስ ውስጥ የሚሠራ በመሆኑ፣ ተጠርጣሪዎቹን በእስር የሚያቆያቸው አለመሆኑን ለፍርድ ቤቱ በማስረዳት፣ በቂ ምክንያቶች አለመሆናቸውንና ተጠርጣሪዎቹም ቀሩ በተባሉት የምርመራ ሒደቶች ላይ ተፅዕኖ ሊያደርሱ ስለማይችሉ ዋስትና እንዲፈቀድላቸው መጠየቃቸውን ጠበቃ አመሐ አስረድተዋል፡፡ ፍርድ ቤቱ የመርማሪ ፖሊሱ ሪፖርት ትክክል ነው ብሎ የሚያምን ከሆነም፣ የመጨረሻ የምርመራ ጊዜ ብሎ ትዕዛዝ እንዲሰጥ መጠየቃቸውን አክለዋል፡፡

ፍርድ ቤቱ ከሌሎቹ ጊዜ በተለየ ሁኔታ ለመርማሪ ፖሊሱ ተገቢ ጥያቄዎችን በማንሳት፣ ቀደም ብሎ ፖሊስ ለተጨማሪ ቀጠሮ ማስፈቀጃ ይጠቀምባቸው የነበሩትን፣ ‹‹ተባባሪ መያዝ ይቀረናል፣ ምስክሮች አልተቀበልንም፣ ሰነዶችን ለትርጉም ልከን አልመጣልንምና አሸባሪዎች ከላኩላቸው ገንዘብ ጋር በተገናኘ ከባንክ ማስረጃ ጠይቀን እየጠበቅን ነው፤›› የሚሉ ምክንያቶችን ማቅረብ እንደማይችል ማስታወቁን ገልጸዋል፡፡

ፍርድ ቤቱ ከላይ ከተጠቀሱት ውጪ ከሆነ ግን ሊቀበል እንደሚችል የሚያሳይ ትዕዛዝ መስጠቱ፣ ፍርድ ቤቱ የምርመራ ሒደቱን ‹‹የመጨረሻ›› ብሎ ለመናገር አለመድፈሩን እንደሚያሳይ ጠበቃ አመሐ ተናግረዋል፡፡ ፍርድ ቤቱ ጉዳዩን በግልጽ ችሎት ለምን ማየት እንዳልቻለ የተጠየቁት ጠበቃ አመሐ፣ በዝግ ችሎት መታየቱን ፖሊስ የሚፈልገው ቢሆንም፣ ፍርድ ቤቱ ግን ‹‹ዝግ ችሎት ነው›› አለማለቱን ገልጸዋል፡፡ ነገር ግን ችሎቶቹ በጣም ጠባብ መሆናቸውን እሳቸውም እንደተገነዘቡ አስረድተዋል፡፡

ከተጠርጣሪዎቹ መካከል አንዱ ጋዜጠኛ አስማማው ኃይለ ጊዮርጊስ፣ የወገብ ሕመም እንዳለበት በተደጋጋሚ ገልጾ ወንበር እንዲሰጠው ቢጠይቅም፣ ምላሽ የሚሰጠው እንዳጣ ለፍርድ ቤቱ በማስረዳት ትዕዛዝ እንዲሰጥለት ጠይቆ፣ ፍርድ ቤቱ ‹‹በጤና በኩል ምንም ድርድር የለም›› በማለት የምርመራ ማዕከሉ እንዲፈጽም ትዕዛዝ ማስተላለፉንም አስረድተዋል፡፡ ቤተሰብም የመጐብኘት መብት እንዳለው ፍርድ ቤቱ አስረድቶ፣ ይኼም ተግባራዊ እንዲሆን ትዕዛዝ መስጠቱን አክለዋል፡፡

አንዳንድ የአስተዳደራዊ ችግሮች ካልሆኑ በስተቀር የምርመራ ማዕከሉ ሁሉንም ተገቢ የሚባሉ ነገሮችን እንደሚያደርግ መርማሪ ፖሊሱ ገልጾ፣ የፍርድ ቤቱን ትዕዛዝ እንደሚያከብርም መናገሩን ጠበቃ አመሐ ለታዳሚዎች አስረድተዋል፡፡ በመጨረሻም ፍርድ ቤቱ ፖሊስ የጠየቀውን ተጨማሪ የ28 ቀናት ጥያቄ በመፍቀድ ለሐምሌ 5 ቀን 2006 ዓ.ም. ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡

Source: Ethiopian Reporter

ኢትዮጵያና ግብጽ በተባበሩት መንግስታት የጸደቀውን የውሃ ኮንቬንሽን ሳይፈርሙ ቀሩ

$
0
0

EthiopiaBlueNileFallsድንበር ተሻጋሪ ወንዞችንና የከርሰ ምድር ውሃዎችን በሀገሮች መካከል እንዴት በጋራ መጠቀም እንደሚችሉ የሚደነግገው የተባበሩት መንግስታትን የውሃ ኮንቬንሽን ኢትዮጵያና ግብፅ ሳይፈርሙ መቅረታቸውን ዛሬ በአዲስ አበባ ታትሞ የወጣው ሰንደቅ ጋዜጣ ዘገበ።

እንደ ጋዜጣው ዘገባ ከሆነ እ.ኤ.አ. ከ1997 ጀምሮ ሀገራት እየፈረሙ እንዲያፀድቁት ክፍት ሆኖ የቆየ “Convention on the Law of the Non Navigational Uses of International Watercourses” የሚለውን ኮንቬንሽን ግብፅና ኢትዮጵያ ግን ሳይፈርሙ ቀርተዋል። ሁለቱ ሀገሮች ይህን ኮንቬንሽን ባይፈርሙም ባለፈው እ.ኤ.አ ግንቦት ወር 2014 በተባበሩት መንግስታት ፀድቆ አለም አቀፍ ኮንቬንሽን ሆኗል።

በዚሁ ዙሪያ ማብራሪያ እንዲሰጡ ሰንደቅ ጋዜጣ የጠየቃቸው በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ፖለቲካል ሳይንስና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ተባባሪ ፕሮፌሰር ዶክተር ያዕቆብ አርሳኖ ሁለቱ ሀገራት ኮንቬንሽኑን ያልፈረሙበት ሁለት መሰረታዊ ምክንያቶች መኖራቸውን ገልጸው ዶክተሩ ግብፅ ኮንቬንሽኑን ያልፈረመችበት ምክንያት ሲያስረዱ በኮንቬንሽኑ ስምምነት ውስጡ ከሰፈሩት ሀገረጎች መካከል፤ “ሀገራት ተሻጋሪ ወንዞችን ሲጠቀሙ ከሌሎች ተፋሰስ ሀገራት ጋር በሚዛናዊነትና በፍትሃዊነት መሆን አለበት” የሚልው አንቀፅን በማካተቱ ስምምነቱን ላለመፈረም ምክንያት ሆኗታል ብለዋል።

ኢትዮጵያ ለምን እንዳልፈረመች ዶክተር ያዕቆብ ሲገልጹ፤ “አንድ ሀገር ተሻጋሪ ወንዝን ለመጠቀም በቅድሚያ ለተፋሰሱ ሀገራት ማሳወቅ አለበት” የሚል አንቀጽ ፈጽሞ ተቀባይነት ባለማግኘቱ መሆኑን አስረድተዋል።

በተባበሩት መንግስታት የሰፈረው አንቀጽ ከዚህ በፊት በቅኝ ግዛት ዘመን በግብፅና በሱዳን በ1929 እና በ1959 የተፈረመው የናይል ውሃ ስምምነት በተመሳሳይ መልኩ የላይኛው ተፋስስ ሀገሮች ማናቸውንም በናይል ዉሃ ላይ የሚያርጉትን ልማት ቀድመው ለግብፅ ማሳወቅ እንዳለባቸው እንደሚደነገግ ይታወሳል።

በሌላ መልኩ እ.ኤ.አ. በ2010 በዑጋንዳ ኢንቴቤ የተደረሰው የናይል ውሃ ስምምነት እንደሚለው የናይል ውሃን ተፋሰስ ሀገራት ጋር የናይል ውሃን በሚዛናዊነትና በፍትሃዊነት መጠቀም አለባቸው ይላል። ይህን አንቀጽ ግብፅ በጽኑ በመቃወም ስምምነቱን አለመፈረሟም የሚታወስ ነው ሲል ጋዜጣው ዘገባውን ቋጭቷል።

የሁለት ፈረሶች ጥያቄ (ዳንኤል ክብረት)

$
0
0
ዳንኤል ክብረት
ሁለት ፈረሶች እንደነበሩ ተነገረ፡፡ አንደኛው እጅግ ለምለም በሆነ ሰፊ ሜዳ ላይ ተሠማርቶ፣ ሲያሻው ደግሞ በግራ በቀኝ ገብስ ፈስሶለት፣ ሲጠማው የሚጠጣው ውኃ በሜዳው መካከል ኩልል ብሎ እየወረደለት፣ አውሬ እንዳይተናኮለው ዙሪያውን በውሻ እየተጠበቀ ይኖር ነበር፡፡ ሁለተኛው ደግሞ የሣር ዘር ለአመል ያህል ብቻ እዚህም እዚያም በበቀለበት፣ ጭው ባለ ደረቅ ሜዳ ላይ ተሠማርቶ ያገኛትን እየነጨ፣ ከዕለታት በአንድ ቀን ከደጋ የዘነበ ዝናብ በአካባቢው ሲያልፍ የሚያገኘውን ጥፍጣፊ ውኃ እየተጎነጨ፣ ሌትና ቀን ምን ዓይነት አውሬ መጥቶ ይዘነጥለኝ ይሆን? እያለ በሥጋት ይኖር ነበር፡፡
daniel-kibret-300x207

ዳንኤል ክብረት

ምንም እንኳን ሁለቱም ፈረሶች በኑሮ በማይቀራረብ ሜዳ ላይ በመከራና በቅንጦት ተለያይተው ቢኖሩም የኑሮ ጥያቄ ግን አገናኝቷቸው ኖሯል፡፡ ያ እንዲያ በለመለመ መስክ ተሠማርቶ እምብርቱ እስኪነፋ ሆዱ እስኪቆዘር እየበላ ሲተኛ ሲነሣ የሚውለው ፈረስ ‹‹ይኼ ሣር ያለቀ ዕለት፣ ይኼም ውኃ የነጠፈ ጊዜ፣ እነዚህም ውሾች እኔን መጠበቅ ትተው የሄዱ ጊዜ፣ ይኼስ ገብስ የጠፋ ቀን ምን ይውጠኝ ይሆን? ያስ ቀን መቼ ይሆን? ይል ነበር፡፡ ይኼ ጥያቄ ምንጊዜም ይረብሸው ነበር፡፡

 

 ያ በደረቅ ሜዳ ላይ እዚህም እዚያም የበቀለች ሣር እየነጨ ከርሱን ሲደልል የሚውለው ፈረስ ደግሞ ‹‹መቼ ይሆን አልፎልኝ ለምለም መስክ ላይ ውዬ፣ ከፈሰሰ ውኃ እንደ ልቤ ተጎንጭቼ፣ ያለ ሥጋት አድሬ የሚነጋልኝ? ያ ቀን መቼ ይሆን?ይል ነበር፡፡

እዚህ ሀገር ያለን ሰዎች በሁለቱ ፈረሶች ጥያቄ ውስጥ ወድቀናል፡፡ አንደኛው መስኩ ለምልሞለት፣ ውኃው መንጭቶለት፣ ሥጋቱ ጠፍቶለት፣ ሕይወቱ ቀንቶለት የሚኖረው ሰው ጥያቄ ነው፡፡ እንዴት ሜዳው ላይ እንደደረሰ አያውቀውም፤ ብቻ አንድ ቀን ተቀለጣጥፎም፣ ተጣጥፎም፣ ተለጣጥፎም፣ ራሱን ሜዳ ላይ አግኝቶታል፡፡ ለስንትና ስንት ፈረስ የሚበቃውን መስክ ብቻውን ተሠማርቶበታል፡፡ አገር የሚያጠጣውን ወንዝ ብቻውን ይንቦራችበታል፡፡ ጥጋብን ከልኩ በላይ፣ ምቾትንም ከመጠን አልፎ ቀምሶታል፡፡ ድህነትን ረስቶ የት መጣውን ዘንግቶታል፡፡ ግን ሥጋት አልለቀቀው ይኼ መሥመር የተበጠሰ ዕለት፣ ይኼ ሥርዓት ያለፈ ቀን፣ ከእገሌ ጋር የተጣላሁ ጊዜ፣ ቀን የዞረችበኝ ሰዓት፣ የተነቃ ለታ፣ ዕቁቡ የተበላ ጊዜ፣ ካርታው ያለቀ ቀን፣ መንገዱ የታወቀ እንደሆን፣ ሕግ የተቀየረ ቀን፣ ምን ይውጠኝ ይሆን? ያችስ ቀን መቼ ትሆን? እያለ ይጠይቃል፡፡ እየበላ ይሠጋል፣ እየጠጣም ይጨነቃል፤ አይቷል፣ ሰምቷል፡፡ ድንገት ለምለሙ ሜዳ ላይ ተገኝተው ድንገት ከሜዳው የጠፉ አሉና፡፡
አሁን ሆዱ ተቀይሯል፤ አንገቱ ተቀይሯል፤ እጁ ተቀይሯል፤ መቀመጫው ተቀይሯል፤ ማረፊያና መዋያው ተቀይሯል፡፡ ይህንን ያጣ ዕለት ምን ይውጠዋል?
ያኛውም ፈረስ አለ፡፡ እንደ ዐርባ ቀን ዕድል ሆኖ የደረቀ መስክ ላይ ውሎ እንዲያደር የተፈረደበት፤ ቢሄድ ቢመጣ፣ ቢወርድ ቢወጣ ከዚያ መስክ መላቀቅ ያቃተው፡፡ መቼ ይሆን የእኔስ ሜዳ በሣር ተሞልቶ እንደነዚያ ሣር የምጠግበው እያለ ምኞት የገደለው፡፡ የእኔስ ወንዝ መቼ ይሆን ውኃ ሞልቶት ሳልጨነቅ የምጠጣው? እያለ ሃሳብ ያናወዘው፡፡ የእርሱ ቤት እየፈረሰች ከጎረቤቱ ዘጠኝ ፎቅ ሲበቅል አይቷል፡፡ ስትተከል፣ ውኃ ስትጠጣ፣ አላያትም፡፡ እንዲሁ ብቻ ፎቋ በቀለች፡፡ ስትገዛ ያላያት፣ ፍንጥር ያልጠጣባት መኪና እንዲሁ ሽው እልም ስትል አያት፤ እናም ምን ዓይነት ፈረሶች ይሆኑ ለዚህ የሚበቁት እያለ ይጠይቃል፡፡ ዝርያቸው ምን ቢሆን ነው? መልካቸውስ ምን ቢሆን ነው? የፈረስ ጉልበታቸውስ ምን ያህል ቢሆነ ነው? ፍጥነታቸውና ቅልጥፍናቸውስ እንዴት ያለ ቢሆን ነው? ጌቶቻቸውንስ እንዴት አድርገው ቢያገለግሏቸው ነው? እንዲህ ለምለም መስክ ላይ የለቀቋቸው? እኛም ስናገለግል ኖረናል፤ ጋሪ ስንጎትት፣ እህል ስንሸከም፣ ዕቃ ስናጓጉዝ ኖረናል፤ ጌቶቻችን ሲጋልቡን ኖረናል፤ ግን እነርሱ ምን ያህል ቢያስደስቷቸው ነው ይህንን ዕድል የሰጧቸው? እያለ ይጠይቃል፡፡
ለመሆኑ እነርሱ ናቸው ወደ እኛ የሚመጡት ወይስ እኛ ነን ወደ እነርሱ የምንሄደው? ለመሆኑ የኛን ድህነት ነው ወይስ የእነርሱን ሀብት ነው የምንካፈለው? በርግጥ ከኛም የሄዱ አሉ፤ ከእነርሱም የሚመጡ አሉ? ይላል፡፡ አንዱ ሜዳ ላይ ተሠማርተን እንደ አቅማችንና እንደ ችሎታችን መጋጥ ሲገባን ለምን ሁለት ዓይነት ሜዳ ሆነ፡፡ አሁን እኛና እነርሱ እኩል ‹‹ፈረስ›› ተብለን እንጠራለን? እኛ ‹‹ሌጣ ፈረስ›› ነን፣ እነርሱ ደግሞ ‹‹ባለ ወግ ፈረስ›› ናቸው፡፡
ግን ይሁን፤ እሺ መቼ ይሆን እኛስ እንደነርሱ የምንሆነው? መቼ ይሆን ያለ ሥጋት ውለን የምናድረው? ለምለሙን መስክ ማን ይነካዋል፤ ላለው ነው ድሮም የሚጨመርለት፤ የኛ የድኾቹን መስክ ነው ለሀብታሞቹ የሚሰጡት፤ የድኾቹን ደረቅ መስክ ሀብታሞቹ የሚቀኑበትን ያህል እኛ በእነርሱ ለምለም መስክ አንቀናም፡፡ ደግሞ አንድ ቀን ይመጣሉ፡፡ ‹‹ይህንን መስክ ለምለም ማድረግ እንፈልጋለን›› ይላሉ፡፡ እኛም ደስ ይለናል፡፡ የዘመናት ምኞታችን አይደል? መንገዱ ጠፍቶን እንጂ እኛም ለምለም ማድረግ እንፈልግ ነበርኮ? መንገዱን ያወቀው ሰው ሲመጣ ለምን እንቃወመዋለን፡፡
ግን ይቀጥሉና ሌላ ነገር ይሉናል፡፡ ‹‹መስኩን ግን ለምለም የምናደርገው ለእኛ እንጂ ለእናንተ አይደለም›› ይሉናል፡፡ ለምን? ለምን? እኛ ለምለም ሣር አይወድልንም? እኛ ለምለም የምናደርግበትን መንገድ ለምን አያሳዩንም? ባያሳዩንስ ለምን አይፈቅዱልንም? ባይፈቅዱልንስ ለምን አይተውንም? እንላለን፡፡ ይህ ግን ጥያቄ ነው እንጂ መልስ የለውም፡፡ እኛም ጥያቄውን የምናውቀውን ያህል መልሱን አናውቀውም፡፡ ስንጠይቅም ‹‹ምላሽ›› እንጂ ‹‹መልስ›› የሚሰጥ አናገኝም፡፡
እኛም ከዚያ መስክ እንወጣለን፣ ወደሌላ መስክም እንዛወራለን፤ አሁንም ቅንጥብጣቢ ሣር እንፈልጋለን፤ ጥፍጣፊ ውኃ እናስሳለን፡፡ ያ እኛ የነበርንበት መስክ ግን በአንድ ጊዜ ይለመልማል፡፡ ውኅው ጅረት ሆኖ ይፈስበታል፡፡ ይገርመናል፡፡ እኛ እዚያ ሳለን፡፡ ውኃ አልነበረም፡፡ እንደ ወር በዓል ቀን ቆጥረን ነበር የምናገኘው፡፡ አሁን ግን ይንፎለፎላል? ለመሆኑ እኛ ምን ብለን መጠየቅ ነበረብን? ይኼ ራሱ ሌላ ጥያቄ ይሆንብናል፡፡ መቼ ይሆን እኛስ እንዲህ ባለው መስክ ላይ የምንሠማረው? እንላለን፡፡ የማይሳካ ምኞት እንመኛለን፤ የማይመለስ ጥያቄ እንጠይቃለን፡፡
እዚያም ቤት ሌላ ጥያቄ አለ፡፡ ፀሐይዋ እንደወጣች ትቀጥል ይሆን? ወንዙ እንደፈሰሰ ይቀጥል ይሆን? ነፋሱ እንደነፈሰ ይቀጥል ይሆን? ሣሩ እንደለመለመ ይዘልቅ ይሆን? እኔስ እንደተወደድኩና ሞገስ እንዳገኘሁ እኖር ይሆን?
ሰውየው ስለ አውሮፕላን አነዳድ የሚገልጥ ማኑዋል አገኘና አውሮፕላኑን አስነሥቶ አበረረ፡፡ ገጹን ይገልጣል፤ የተጻፈውን ይፈጽማል፤ አውሮፕላኑም ይበራል፡፡ በቀጣዩ ገጽ ላይ ምን እንዳለ የሚያውቀው ነገር አልነበረም፡፡ ገጹ ተገንጥሎ ቢገኝ ምን ማድረግ እንዳለበትም የሚያውቀው ነገር አልነበረም፡፡ ብቻ ይገልጣል፣ ያነባል፣ ይነካካል፣ ይበራል፡፡ አውሮፕላኑ ተነሥቶ በሃያ አምስት ሺ ጫማ ከፍታ ላይ ሲደርስ የመጨረሻው ገጽ ላይ ደረሰ፡፡ ‹‹ክፍል ሁለትን በክፍል ሁለት መጽሐፍ ይመልከቱ›› ይላል፡፡ ክፍል ሁለት መጽሐፍ ግን የለውም፤ የት እንዳለም አያውቅም፡፡ ምን ማድረግ እንዳለበትም አልተዘጋጀም፡፡ ስለዚህም እንደወጣ መውረድ ጀመረ፡፡ ያውም በዝግታ ሳይሆን እየተምዘገዘገ፡፡
እናም እኛ በለምለም መስክ ላይ ያለን ፈረሶች፣ አንድ ክፉ ቀን መጥቶ ‹‹ክፍል ሁለትን በሌላ መጽሐፍ›› ቢለንስ? ምን ይውጠናል? ለመሆኑ ክፍል ሁለት የት ነው ያለው? እስካሁን ያሳየን የለም፡፡ እኛ የምናውቀው የየዕለቱን ምዕራፍ ብቻ ነው፡፡ ያንን እናነባለን፣ በእርሱ እንኖራለን፣ ቀጣዩን ምዕራፍ አናውቀውም? ስለዚህም እኛም እንጠይቃለን? እንዲሁ እንዘልቅ ይሆን? ብለን፡፡

© ይህ ጽሑፍ በአዲስ ጉዳይ መጽሔት ላይ የወጣ ነው

Source: Danielkibret


‹‹ይህ ሽልማት የእኔ ብቻ አይደለም፣ የእናንተም ነው›› እስክንድር ነጋ (ኤልያስ ገብሩ ጎዳና)

$
0
0

በኤልያስ ገብሩ ጎዳና

‹‹ይህ ሽልማት የእኔ ብቻ አይደለም፡፡ የእናንተም ነው፡፡ …››
‹‹በእስር ላይ የምትገኙ ጋዜጠኞች እና ጦማሪያኖች የእኔ ጀግኖች ናችሁ››

ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ

‹‹አሁን ደስተኛ ነኝ››
‹‹እስክንድርን ምግብ ማብሰል እያለማመድኩት ነው››

አቶ አንዷለም አራጌ

ከትናንት በስትያ ሰኔ 03 ቀን 2006 ዓ.ም ከቀኑ 6፡00 ሰዓት ላይ ከቅርብ ጓደኛዬ እና የሙያ ባልደረባዬ ጋዜጠኛ አናንያ ሶሪ ጋር ወደቃሊቲ ማረሚያ ቤት [እስር ቤትም ነው] አምርተን ነበር- ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋንና የአንድነት ፓርቲ ጸሐፊ የሆኑትን አቶ አንዷለም አራጌን ለመጠየቅ፡፡ የተለመደውን የፖሊስ ፍተሻ አልፈን ወደ ውስጥ ስንዘልቅ የሰማያዊ ፓርቲ የድርጅት ጉዳይ ኃላፈ አቶ ብርሃኑ ተ/ያሬድ ፣ አቶ ሳሙኤል የተባሉ አባልና የ‹‹ነገረ ኢትዮጵያ›› ጋዜጣ ዋና አዘጋጅ ጋዜጠኛ ጌታቸው ሽፈራው እስክንድርን ሊጠይቁ ቀድመውን ደርሰው ነበር፡፡Andualem & Eskinder with family

…እስክንድርን እና አንዷለምን አስጠራናቸው፡፡ ሁለቱም ሲያዩን ደስ አላቸው፡፡ በተለይ በተለይ የእስክንድር ፈገግታ በጣም ደማቅ ነበር፡፡ ተከፋፍለን ከሁለቱም ጋር ሃሳቦችን መለዋወጥ ጀመርን፡፡

እስክንድር በዓለም የጋዜጠኞች እና የዜና አታሚዎች ማኅበር የዓመቱ የወርቅ ብዕር የ “pen Golden of freedom 2014″ ተሸላሚ በመሆኑ ‹‹እንኳን ደስ ያለህ›› አልኩት፡፡ ‹‹አመሰግናለሁ፡፡ ትናንት አንድ ልጅ ሊጠይኝ መጥቶ ነግሮኛል›› ካለን በኋላ ደግመን ስለሽልማቱ በጋራ ሃሳብ መለዋወጥ ቀጠልን፡፡ እስክንድር ሽልማቱ አዲስ መሆኑን አላወቀም ነበር፡፡

በመሆኑም ስለሽልማቱ ሁኔታ፣ ማን እንደሸለመው፣ ሽልማቱ የት እንደተደረገ፣ ሽልማቱን ማን እንደተቀበለለት [ሽልማቱን የተቀበለው በኢትዮጵያ በሽብርተኝነት ክስ ወንጀለኛ ተብሎ ከባልደረባው ፎቶ አንሺ ጋር 11 ዓመታት ከተፈረደበት በኋላ በይቅርታ የተለቀቀው ስዊድናዊ ጋዜጠኛ ማርቲን ሽብዬ ነበር]፣ የሽልማት ሥነ-ሥርዓቱ ምን እንደሚመሰል፣ በሽልማቱ እነማን እንደተገኙ …ያወቅነውን ሁሉ ነገርነው፡፡

‹‹ይህንን አላዋኩኝም፣ ሰርካለም (ባለቤቱ) ለምን በቦታው አልተገኘችም?›› በማለት ጠየቀንና በድጋሚ ደስ ብሎት ጣቶቹን በሽቦ ውስጥ አሾልኮ ጨበጠን፡፡ ወዲያው ይህቺን መልዕክት ተናገረ፡-

‹‹ይህ ሽልማት የእኔ ብቻ አይደለም፡፡ የእናንተም ነው፡፡ የኢትዮጵያዊ ጋዜጠኞች ነው፡፡ ሁላችንንም ይመለከተናል፡፡ ለሁላንችም ይገባናል፡፡ ይሄንን ሽልማት የምመለከተው ሐሳብን በነጻነት ከመግለጽ የመብት ጥሰት አኳያ ብቻ አይደለም፡፡ ለሌሎች የዜጎች መብቶች ሲሉ ለታገሉ እና እየታገሉ ላሉ ፖለቲከኞች፣ የሕሊና እስረኞችም ጭምር ነው፡፡ ሀሳብን በነጻነት የመግለጽ መብት ከሌሎች ከተነፈጉ መብቶች ተለይቶ የሚታይ አይደለም፡፡ ሁሉንም መብቶች እናገኛቸዋለን፣ ወይም እናጣቸዋለን፡፡ ለዚህ ደግሞ ጸንተን እንታገል፣ ትግላችን ግን ሰላማዊ ብቻ መሆን አለበት፡፡ …››

እስክንድር ደስ ብሎት ሃሳቡን መናገሩን ቀጥሏል፡፡ እኔ ለተወሰኑ ቀናት በማዕከላዊ መታሰሬን ሰምቶ ስለነበረም ‹‹ማዕከላዊ እያለህ የታሰሩትን ጋዜጠኞች እና ጦማሪያኖች ለማግኘት ችለህ ነበር?›› ብሎ ጠየቀኝ፡፡ እነሱን በአካል ማግኘት አለመቻሌን ነገር ግን ከእነሱ ጋር ታሥረው የነበሩ ሌሎች ተጠርጣሪ ዜጎችን አግኝቼ በእስር ስላሉበት ሁኔታ መጠየቄን ነገርኩት፡፡

የታሰሩት ጋዜጠኞች እና ጦማሪያኖችን ቤተሰብ ማግኘት እችል እንደሆነና ከቻልኩም በእነሱ በኩል መልዕክቱ ይደርስለት ዘንድ በድጋሚ ጥያቄያዊ ሃሳቡን አቀረበልኝ፡፡ የተወሰኑ የእስረኛ ቤተሰቦችን ማግኘት እንደምችል አስረዳሁት፡፡

‹‹የታሰራችሁ ጋዜጠኞች እና ጦማሪያኖች የእኔ ጀግኖች ናችሁ፡፡ አከብራችኋላሁ፡፡›› ብለህ ንገርልኝ አለኝ – ደጋግሞ፡፡ …

በዕለቱ ከሰዓታት በፊት ሰናይት ታከለ የምትባል ወዳጄም እስክንድርን ልጠይቀው ቃሊቲ እንደምሄድ በነገርኳት ጊዜ ‹‹እንደማከብረው እና እንደማደንቀው ንገርልኝ›› ያለችኝን መልዕክት ለእስክንድር አደረስኩላት፡፡

እሱ ግን ሳቅ እያለ ‹‹ተሳስተሻል! …ተሳስተሻል! …ተሳስተሻል›› ብለህ ንገራት አለኝ፡፡ ‹‹ለምን?›› አልኩት፡፡ ‹‹ገና ምን ሰርቼ?›› በማለት በዚያ ትሁት አንደበቱ መለሰልኝ፡፡ በእውነት መልሱ አስደመመን፡፡ ዋይ እስክንድር፣ ፍጹም የተለየ ታላቅ ሰው!!!

እስክንድርን እናናግረው የነበርን ጠያቂዎች ወደ አንዷለም አራጌ ዞርን፡፡ አንዷለም ጋር የነበሩት ደግሞ ወደ እስክንድር፡፡

አንዷለም የስፖርት ቲ-ሸርት ከቁምጣ ጋር ለብሷል፡፡ ጥቁር መነጽር አድርጓል፡፡ ረጋ ብሎ ፈገግ በማለት ‹‹ምን አዲስ ነገር አለ?›› በማለት ጨዋታ ጀመረ፡፡ አንዷለም የእስክንድርን ሽልማት ሰምቶ ኖሮ፣ ‹‹አሁን ከምሳ በኋላ ጣፋጭ የለውዝ ሻይ እሱን እና ጓደኞቻችንን በመጋበዝ ‹እንኳን ደስ ያልህ!› በማለት ሰርፕራይዝ አደርገዋለሁ፡፡ ምግብ ማብሰል እያለማመድኩት ነው፡፡ ብዙ ጊዜ እኔ ነኝ ሰርቼ የማበላው፡፡ በልጅነቱ በበርገር ያደገ ልጅ አሁን ሽንኩርት እና ቲማቲም መክተፍ ችሏል …›› በማለት በቀልድ ነገረን፡፡

‹እነማን ከእናንተ ጋር አሉ? በአንድ ክፍል ውስጥስ ስንት ናችሁ? ጊዜያችሁንስ እንዴት ነው የምትጠቀሙበት?›› የሚል ጥያቄ አቀረብንለት፡፡

‹‹ለረዥም ጊዜ፣ በጣም አስቸጋሪ ክፍል ውስጥ፣ መሬት ላይ ስንከባለል ነበር በእስር ያሳለፍሉት፡፡ አሁን አቶ ስዬ አብርሃ ታስሮ በነበረበት ጥሩ በሚባል ክፍል ውስጥ ለአምስት ታስረን እንገኛለን፡፡ አቶ መላኩ ተፈራ፣ አቶ መላኩ ፈንታ ና አንድ ባለሃብት አብረውን ናቸው፡፡ አሁን አልጋ ላይ መተኛት ጀምሬአለሁ፡፡ ይሄ ለእኔ እንደ አዲስ ሕይወት ነው፡፡ አሁን ደስተኛ ነኝ፡፡ …ጊዜያችንን በጥሩ ሁኔታ ከፋፍለን እየተጠቀምንበት ነው፡፡ እናነባለን፣ እንወያያለን፣ የምንፈልጋቸውን መጽሐፍት ግን በምንፈልገው ጊዜ አናገኝም፣ በዚህ በኩል መጠነኛ ችግር አለ፡፡ በተረፈ ደህና ነኝ፡፡ እኔ ተስፈኛ ነኝ፡፡ እናንተም በተሰማራችሁበት ዘርፍ የምትችሉትን ሁሉ ለሀገራችሁ ለውጥ መታገል አለባችሁ…››

ከሁለቱም ጋር የነበረንን የ30 ደቂቃ ቆይታ ሳንጠግብ ‹‹በቃችሁ›› የሚለው የፖሊስ ድምጽ ተሰማ፡፡ ‹‹እናመሰግናለን፣ በቃ ሂዱ›› ሲል አንዷለም በእርጋታ ተናግሮ በሽቦ ስር አሾልኮ እጆቻችንን ጨበጠን፡፡

እስክንድር ደግሞ ‹‹‹ሲመቻችሁ ብቻ መጥታችሁ ጠይቁን፣ ሥራ እንዳይበደል!፡፡ ሥራችሁን ሥሩ›› በማለት ለእኛም ያለውን አሳቢነት ከምክሩ ጋር ደጋግሞ ገለጸልን – ሁሉንም ሰላም በሉልኝ በማለት፡፡ እንግዲህ እስክንድርን የምትሉ ሁሉ ሰላምታውን በእኔ በኩል አድርሻለሁ፡፡

በነፋስ ስልክ ላፍቶ ከተማ ቤቶች መፍረስ ጀመሩ፤ ፖሊስ እሪ ያሉ ወጣቶችን በቆመጥ ደበደበ

$
0
0
ፖሊስ እና የአካባቢው ወጣት ተፋጦ

ፖሊስ እና የአካባቢው ወጣት ተፋጦ

(ዘ-ሐበሻ) ነፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ወረዳ 1 ቀበሌ 1 በተለምዶ ስሙ ሃና ማርያም ጀርባ በሚገኘው ልዩ ስሙ ቃሬሳና ኮንቶማ ሰፈር ወደ 5000 የሚጠጉ ቤቶችን መንግስት ለማፍረስ ቀይ ቀለም የቀረባ ሲሆን ክፍለከተማውን ነዋሪውን አናውቃችሁም ትነሳላችሁ ማለቱን ተከተሎ ከ 1000 በላይ ኢትዮጵያውያን መድረሻ አጣን በሚል የኢሕ አዴግ ተለጣፊ ነው ወደ ሚባለው ወደ ኢትዮጵያ ሰብአዊ መብት ኮሚሽን በማምራት ሰልፍ የወጡ ሲሆን፤ ኮሚሽነሩ የኢትዮጵያ ቴሌቭዥን መጥቶ ቪድዮ እስከሚቀርጽ ድረስ ከተበቁ በኋላ የሕዝቡን እሪታ “የሰብአዊ መብት መጣስ ጉዳይ መሆኑን ወደ ፊት የምናየው ይሆናል፤ ለአሁኑ ግን 10 ኮሚቴ መርጣችሁ ተነጋግረን መልስ እንሰጣችኋለን” ማለታቸውን የዘ-ሐበሻ ዘጋቢዎች ከአዲስ አበባ አስታውቀዋል።

የጉዳዩ ባለቤቶች ከአዲስ አበባ በፎቶ ግራፍ አስደግፈው በላኩልን መረጃ መሰረት በነፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ቤት ማፍረሱ የተጀመረ ሲሆን ሕዝቡ ካለምንም መተኪያ መድረሻ አታሳጡን እያለ እሪታውን ቢገልጽም ፖሊስ በአካባቢው መጥቶ ወጣቶችን በቆመጥ እንደደበበደ ታውቋል። በአካባቢው ያለው ውጥረት አሁንም እንደቀጠለ ሲሆን ሕዝቡ እየተቃወመ መንግስትም ካለምንም መተኪያ “አናውቃችሁም፤ ከአካባቢው ልቀቁ” በሚል ማፍረሱን መቀጠሉን ነዋሪዎቹ ለዘ-ሐበሻ ጠቁመው፤ ወጣቶቹም ከፖሊስ ጋር ግብግብ ላይ መሆናቸውን ገልጸውልናል።

 

ጦማሪያኑን እና ጋዜጠኞቹን በተመለከተ ችሎቱ ለፖሊስ ጠንካራ ትዕዛዝ አስተላለፈ

$
0
0

በ አሸናፊ ደምሴ

በቁጥጥር ስር ከዋሉ ባለፈው ቅዳሜ (ሰኔ 7 ቀን 2006 ዓ.ም) 50ኛ ቀናቸውን በእሰር ያሳለፉት ስድስቱ ጦማሪያንና ጋዜጠኞች ለአራተኛ ጊዜ የ28 ቀን የጊዜ ቀጠሮ ተፈቅዶባቸዋል። ለአራተኛ ጊዜ ፍርድ ቤት የቀረቡት ከዞን 9 ጦማሪያን መካከል ዘላለም ክብረት፣ ናትናኤል ፈለቀና አጥናፉ ብርሃኔ ሲሆኑ፤ ጋዜጠኞቹ ደግሞ ተስፋለም ወልደየስ፣ ኤዶም ካሳዬ እና አስማማው ወ/ጊዮርጊስ ናቸው። በዕለቱ ችሎቱ መርማሪ ፖሊስ የሚያቀርባቸውን ተደጋጋሚ ምክንያት አጠንክሮ በመፈተሽ በቀጣይ ቀጠሮ ፈፅሟቸው ሊመጣ የሚገቡ አራት ተግባራትን በግልፅ በማስቀመጥ ትዕዛዝ ሰጥቷል።
zone 9999
በፌዴራሉ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ 1ኛ ወንጀለ ችሎት በዕለቱ የቀረቡት ጦማሪያንና ጋዜጠኞች ፖሊስ የመሰረተባቸውን የሽብርተኝነት ክስ በተመለከተ የደረሰበትን ማስረጃዎች ለፍርድ ቤቱ ለማሰማት ነበር። በችሎቱ ጥበት ምክንያት አንዳችም የውጪ ሰው ወደ ውስጥ ሳይዘልቅ የተከናወነው ችሎቱ በብዙዎች ዘንድ “የዝግ ችሎት ነው ወይ?” የሚያሰኝ ጥያቄን ቢያስነሳም ለጦማሪያኑና ጋዜጠኞቹ በጥብቅና የቆሙት ጠበቃ አመሃ መኮንን ግን ችሎቱ ጠባብ በመሆኑ ነው የሚል ምላሽ ሰጥተዋል። በዕለቱ በግቢው ውስጥ በርካታ ቁጥር ያላቸው ጋዜጠኞች ዲፕሎማቶችና የታሳሪዎቹ ወዳጅ ዘመዶች ተገኝተው ነበር።

ፍርድ ቤቱ የማዕከላዊ ፖሊስ በታሳሪዎቹ ላይ ካለፈው ቀጠሮ መልስ አገኘዋቸው የሚላቸውን መረጃዎችና ሰራዋቸው የሚላቸውን ተግባራት በተመለከተ ለፍርድ ቤቱ ሲያስረዳ፤ በከፊል ሰነዶችን ማስተርጐሙን፤ በከፊል የባንክ ማስረጃዎችን ማግኘቱንና በከፊል የቴክኒክ ማስረጃዎችን ስለማሰባሰቡ ቢገልፅም በደፈናው ግን “ብዙ ስራ ሰርተናል፤ ብዙ ስራም ይቀረናል” ሲል ለፍርድ ቤቱ ማስታወቁን ጠበቃው ከችሎት መልስ ተናግረዋል።

በዚህም ጉዳይ ላይ ፍርድ ቤቱ ማስረጃዎች ሲቀርቡ፤ በጥቅል መቅረብ እንደሌለባቸውና በዝርዝር እንዲቀርብለት ትዕዛዝ የሰጠ ሲሆን፤ ከዚህ በኋላም ጥቅል ማስረጃን ማድመጥ እንደማይፈልግ አስታውቋል። ፖሊስ ለስራው መጓተት አሁንም እንደቀደመው ጊዜ ካቀረባቸው ምክንያቶች ውስጥ የምስክሮችን ቃል ስለአለመቀበሉ፤ ተባባሪዎችን በቁጥጥር ስር ለማዋል መቸገሩንና ወደ ክልል ሀገር ሄደውብኛል በሚል አባሎቹን ልኮ በቁጥጥር ስር ለማዋል እየተከታተለ መሆኑን ከመግለፁም በተጨማሪ አሁንም ሰነዶችን አስተርጉመን አልጨረስንም ሲል አብራርቷል።

የተከሳሽ ጠበቆች በበኩላቸው ለፍርድ ቤቱ ሲያስረዱ ለአራተኛ ጊዜ በጊዜ ቀጠሮ ፍርድ ቤት መቅረባቸውን አስታውሰው፤ የቱንም ያህል ውስብስብ ወንጀል ቢሆን ተጠርጣሪዎቹ እጃቸው ከተያዘበት ጊዜ ጀምሮ ያለው 50 ቀናት በቂ ናቸው የሚል መከራከሪያ አሰምተዋል። ጠበቃው አክለውም ይህ የሚያሳየው ፖሊስ ከመነሻው አንድም ማስረጃ ሳይሰበስብ ልጆቹን የያዛቸው መሆኑና ይህም ሕግን የጣሰ ተግባር ነው ሲሉ አስረድተዋል። ሌላው በጠበቆች በኩል የቀረበው አቤቱታ ፖሊስ በተደጋጋሚ የሚያነሳቸው ተመሳሳይ ምክንያቶች በመሆናቸው የቀረቡትን ምክንያቶች ውድቅ አድርጐ ተጠርጣሪዎቹን በዋስ እንዲለቅ፤ አልያም ፍርድ ቤቱ ሕጋዊ ምክንያት አለኝ ብሎ የሚያምን ከሆነ ይህ የመጨረሻ የጊዜ ቀጠሮ ይሁንልን ሲሉ ስለመጠየቃቸው ጠበቃው ተናግረዋል።

የግራ ቀኙን ኀሳብ ያዳመጠው ፍርድ ቤቱም፤ ፖሊስ በተደጋጋሚ ከሚያነሳቸው ምክንያቶች ውስጥ አራት ጉዳዮችን በመምረጥ በቀጣዩ ቀጠሮ እልባት ሰጥቷቸው እንዲመጣ ትዕዛዝ የሰጠ ሲሆን፤ እነዚህ አራት ተግባራትም ተባባሪዎቻቸውን አልያዝንም፣ የምስክሮችን ቃል አልተቀበልንም፣ ሰነዶች ተተርጉመው አልመጡልኝምና ከሽብርተኝነት ጋር በተያያዘ በባንክ የተላከላቸውን ገንዘብ በተመለከተ ደብዳቤ ጽፈን ምላሽ እየተጠባበቅን ነው የሚሉትን ጉዳዮች በተመለከተ ከዚህ በኋላ ለጊዜ ቀጠሮ መጠየቂያ ምክንያት ሆነው ሊቀርቡ እንደማይችሉ በመግለፅ ትዕዛዝ የሰጠ ሲሆን፤ ይሁን እንጂ ፍርድ ቤቱ የጊዜ ቀጠሮውን የመጨረሻ ነው እንዳላለ ጠበቃው ተናግረዋል።

በሌላም በኩል የተጠርጣሪዎቹ ቤተሰብ እንዳይጠይቃቸው መሰናክል መኖሩንና፤ በተለይም ጋዜጠኛ አስማማው ወ/ጊዮርጊስ የወገብ ሕመም ያለበት መሆኑን በመግለፅ ወንበር ወደክፍሉ እንዲገባለት መጠየቁን ነገር ግን አሁንም ድረስ አለመፈፀሙን ለፍርድ ቤቱ አስረድተዋል። ፍርድ ቤቱም በበኩሉ መርማሪ ፖሊሶቹ በዚህ ላይ ምላሽ እንዲሰጡ ያዘዙ ሲሆን፤ የተጠርጣሪዎቹን ቤተሰብ መጐብኘትን በተመለከተ ከተደራራቢ ስራና ከአስተደደር ጋር የተያያዘ መሆኑን በመጥቀስ የመከልከል ደረጃ ግን አልተደረሰም ሲል የተፈጠሩት ክፍተቶች እንደሚያሻሽሉ አስረድቷል። የጋዜጠኛ አስማማው ወ/ጊዮርጊስን ጥያቄ በተመለከተ ፍርድ ቤቱ በጤና ጉዳይ ላይ ምንም አይነት ድርድር የለም በሚል የሰጠውን ትዕዛዝ ለመፈፀም እንደሚቻል አሳውቀዋል።

የፌዴራሉ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ ችሎት ፖሊስ የጠየቀውና ተጨማሪ 28 ቀናት የምርመራ ጊዜ በመፍቀድ ለሐምሌ 5 ቀን 2006 ዓ.ም እንዲቀርቡ አዟል።

ምንጭ፦ ሰንደቅ ጋዜጣ

የደቡብ ሱዳን ድርድር በ “ስቱፒድ” ምክንያት ተቋረጠ

$
0
0

VOA 1የምሥራቅ አፍሪካ ሃገሮች የጋራ ልማት ትብብር ተቋሙ ኢጋድ አንድ ባለሥልጣን በደቡብ ሱዳን ፕሬዚዳንት ሳልቫ ኪር እና በተቃዋሚው መሪ ሪያክ ማሻር ላይ የዘለፋ ቃል ሠንዝረዋል በሚል በሁለቱ ወገኖች መካከል ይካሄድ የነበረው ውይይት ተቋርጧል፡፡

ውይይቱ የተስተጓጎለው ተቃዋሚዎቹ በሰዓቱ ባለመገኘታቸው ጭምር ነው ሲሉ አንድ የመንግሥቱ ቃል አቀባይ የተናገሩ ሲሆን ተቃዋሚዎቹ ደግሞ የተሟላ ውክልና ስለመኖሩ ሥጋት አለን ብለዋል፡፡

በሌላ በኩል ደግሞ ተቃዋሚዎቹ ባለፈው ዕሁድና በማግስቱም ሰኞ በናስር ከተማ ላይ ጥቃት አድርሰዋል ሲሉ የአፐር ናይል ግዛት ባለሥልጣናት ክስ አሰምተዋል፡፡

ጥቃቱ በደረሰ ወቅት በመረጋጋቱ የተበረታቱ ሰላማዊ ነዋሪዎች ወደ ከተማይቱ እየተመለሱ እንደነበረ ባለሥልጣናቱ አመልክተዋል፡፡

የተቃዋሚዎቹ ቃል አቀባይ ግን የመንግሥቱ ባለሥልጣናት ክሥ “ሃሰት ነው” ብለው እነርሱ ያደረጉት የተፈፀመባቸውን የከባድ መሣሪያ ድብደባ መመከትና ይዞታቸውን መከላከል ብቻ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

በሌላ በኩል ደግሞ ደቡብ ሱዳን ለሚገኘው የተባበሩት መንግሥታት የደቡብ ሱዳን የሰላም ጥበቃ ልዑኩ – ኡንሚስ አዛዥ እንዲሆኑ ኢትዮጵያዊው ሌተና ጀነራል ዮሃንስ ገብረሚካኤል ተሹመዋል፡፡

ፊሊፕ አሊዩ ከጁባ የላከውንና ከሌሎች ምንጮች የደረሱንን ዘገባዎች ሰሎሞን አባተ አቀናጅቶ ያቀርባቸዋል፡፡

ለዝርዝሩ የተያያዘውን ዘገባ ያዳምጡ

Source: voanews

ከምርጫ እርቅ እንዲቀድም ዶ/ር ያዕቆብ አሳሰቡ

$
0
0

yakobኢትዮጵያ የ2007ቱን አገር-አቀፍ ምርጫ ለሌላ ጊዜ አስተላልፋ በቅድሚያ የብሔራዊ እርቅ ጉባዔ መጥራት አለባት ሲሉ ዶ/ር ያዕቆብ ኃይለማርያም ሃሣብ አቅርበዋል፡፡

በ1997ቱ አገር-አቀፍ ምርጫ ወቅት የቅንጅት ለአንድነትና ለዲሞክራሲ አመራር አባል የነበሩትና የህግ ምሁሩ ዶ/ር ያዕቆብ ኃይለማርያም “የአገሪቱ ህልውና ከምንም በላይ ቅድሚያ ሊሰጠው ይገባል»ም ብለዋል።

እስክንድር ፍሬው አነጋግሯቸዋል፡፡ ለዝርዝሩ የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ፡፡

Source: voanews

Viewing all 15006 articles
Browse latest View live