Quantcast
Channel: Ethiopian News | ዘ-ሐበሻ | Latest News Provider | News For All
Viewing all 15006 articles
Browse latest View live

Health: ሁካ (ሺሻ) ምን ይጠቅማል? ምን ይጎዳል?

$
0
0

ሺሻ፣ ሁካ፣ ናርጊሌ፣ ጌሊዮን እንዲሁም በተለያዩ ሀገራት የተለያዩ ስሞችን በመያዝ የሚታወቀው ዕቃ የተለያዩ ቅጠላ ቅጠል፣ ፍራፍሬ፣ የቶባኮ ቅጠል፣ ወይንም ሐሺሽ ለማጨስ የተሰራ ከመስታወት በተሰራና ጠርሙስ መሰል ዕቃ በትቦ አማካኝነት የተፈለገውን የዕፅ አይነት በውሃ ፊልተር አድርጎና ሙቀትን ተጠቅሞ የተፈገለውን ውጤት ለማድረስ የተዘጋጀ ዕቃ ነው፡፡
hukka
ሁካን ለመጀመሪያ ጊዜ የፈጠረው ሐኪም አብዱል ፉት የተባለው ህንዳዊ ሐኪም ሲሆን ይሄም ቶባኮ በጤና ላይ የሚያስከትለውን ችግር ለመቀነስ በመጀመሪያ ጭሱ በውሃ ውስጥ ማለፍ አለበት ብሎ በማሰቡ የተነሳ ነው፡፡ ሺሻ በህንድ ሀገር ውስጥ በሚጠቀሙበት በተለይ በድሮ ጊዜ እንደ ባህል ከመታየቱም በላይ በተወሰነ መልኩ ከሀብት ከክብር ጋርም ይያያዝ ነበር፡፡ ከጊዜም በኋላ ከህንድ ሀገር አልፎ በአብዛኛው የአረብ ሀገሮች ውስጥ ለረዥም ጊዜ መታየት የጀመረው ሺሻ ወደ ሌሎች የዓለም ክፍሎች ብሎም ወደ ሀገራችን መግባቱ አልቀረም፡፡
በአብዛኛው በሀገራችን ላይ የሚታየው የሺሻ አጠቃቀም ከጫት ጋር ተያይዞ ይሁን እንጂ ከጊዜ ወዲህ ሺሻን ለብቻው የሚጠቀመው የሰው ቁጥር እጅግ እየጨመረ ከመሄዱም በላይ በተለይ በወጣቱ ላይ ገኖ መታየቱ ለሁኔታው የበለጠ ትኩረት እንድንሰጠው አድርጎናል፡፡
ሺሻን በተመለከተ የተለያዩ ሀገሮች የተለያየ የመከልከል አጋጣሚ ሲኖረው ይህም የሆነበት ዋናው ምክንያት በጤና ላይ የሚያስከትለው ችግር ከጊዜ በኋላ በጥናት እየታወቀ በመሄዱ ሺሻ በሚጨስበት ወቅት የአጫሹን ብቻ ሳይሆን የህብረተሰቡንም ጤና ሊጎዳ በመቻሉ የተፈጠረ ሁኔታ ነው፡፡

ሺሻ ማጨስ በጤና ላይ ምን አይነት ችግር ሊያስከትል ይችላል

በመሰረቱ ሺሻ ከሲጋራ ያነሰ የጤና ችግር ያመጣል የሚል የተሳሳተ እምነት አለ፡፡ ይሄም የሆነበት ምክንያት በውሃ ውስጥ የሚያልፍ እንደመሆኑና ወደ የአየር ትቦ ሲገባም የመክበዱ መጠን የሲጋራ ያህል ባለመሆኑ ነው፡፡ ነገር ግን በአሁኑ ጊዜ ሺሻ በጤና ላይ የሚያስከትለውን ችግር ለማወቅ በርካታ ጥናቶች በሂደት ላይ ቢሆኑም ዳሩ ግን እስከ አሁን የተደረጉ ጥናቶች የሚያመላክቱት ሺሻ ማጨስ ሲጋራ ከማጨስ የበለጠ ጉዳት እንደሚያስከትል ነው፡፡
- በሺሻ ዕቃ ውስጥ ያለው ውሃ በቶባኮው ውስጥ ያለውን የጤና ጠንቅ ነገሮች አጥልሎ አያስቀረውም፡፡

- በሺሻ አማካኝነት የሚጨሰው ኒኮቲን የተወሰነው ያህል በውሃው ውስጥ ይቅር እንጂ አሁንም ቢሆን ሱስ ለማስያዝና በጤና ላይም ጉዳት ለማስከተል በቂ የሆነ የኒኮቲን መጠን በበቂ ሁኔታ ወደ ሰውነታችን እንደመግባቱ እንደ ማንኛውም አደንዛዥ ዕፅ ሱስ ሊያስይዝ ይችላል ማለት ነው፡፡
- ከሺሻ የሚወጣው ጭስ ከሲጋራ ጋር ሲነፃፀር እኩል ወይንም የበለጠ የካርቦን ሞኖኦክሳይድ እና የታር መጠን እንዲሁም ደግሞ የተለያዩ ከባድ ንጥረ ነገሮችን በብዛት እንደመያዙ የአፍን የአየር ቧንቧ ካንሰር የመከተል እድሉ አሁንም ቢሆን ከፍ ያለ ነው፡፡

- የዓለም የጤና ድርጅት በቅርቡ እንዳሳወቀው የሺሻ አጫሾች አንድ ሲጋራ ወይንም ሲጋራዎች ከማጨስ ይልቅ ረዥም ጊዜ እንደመወሰዳቸው መጠን የሚከሰተው የጤና ችግር እጅግ የጨመረ ነው፡፡ ይሄንንም ስንል የተለመደ የአንድ ሰዓት የሺሻ ማጨስ ከሲጋራ ይልቅ ከ100-200 እጥፍ ለሚሆን የጭስ መጠን ያጋልጣል፡፡ እንዲሁም በአንድ ጊዜ የሚደገውና የሚጨሰው የሺሻ መጠን የሚያስከትለው የጤና ችግር 70 ሲጋራ በማጨስ ከሚከተለው ችግር ጋር ይመጣጠናል፡፡

- በዚህም አማካኝነት ሺሻ ማጨስ ለአፍና ለድድ፣ ኢንፌክሽን፣ ለቲቢ፣ ለአፍ ካንሰር፣ ለአየር ቧንቧ በተለይም ለሳንባ ካንሰር፣ እንዲሁም ለተለያዩ ሁኔታዎች ያጋልጠናል ማለት ነው፡፡
በአጠቃላይም ሲጋራ ማጨስ ለሰውነትና ለጤና የሚጎዳ ነው፤ ሺሻ ማጨስ ደግሞ እንደየሁኔታው ከሲጋራ ማጨስ ባይብስ እንኳን ያነሰ እንደማይሆን ግን እርግጥ ነው፡፡

የተለያዩ ሱስ የሚያስይዙ ኬሚካሎችን የያዙ ነገሮችን ለዚሁ ተግባር ብለን የምንጠቀምባቸው ከማንጠቀምባቸው ሰዎች አሁን አሁን እየጨመርን የመጣን ይመስላል፡፡ ከእነዚህም መካከል አንዱና ብዙ ሰው የሚጠቀምበት ሲጋራ ይገኛል፡፡ በሲጋራ ውስጥ የሚገኘው ቶባኮ የሚባለው የቅጠል አይነት በውስጡ ኒኮቲን የተባለ ሱስ የሚያስይዝ ኬሚካል እንደመኖሩ መጠን ይሄንን የቶባኮ ቅጠል በተለያየ መልኩ ለሱስ ማርኪያነት መጠቀም ከተጀመረ በርከት ያሉ ዘመናትን አስቆጥሯል፡፡

ነገር ግን ይህ የቶባኮ ቅጠል ከሲጋራ መልኩ ማጨስ የተጀመረው በ20ኛው ክፍለ ዘመን ሲሆን የሲጋራ አጫሽ ቁጥር መጨመሩም ሆነ በሲጋራ ምክንያት የሚመጡት ችግሮች መብዛታቸው በቅርቡ የመጣና እየታየ ያለ ችግር ነው፡፡ ያልተቃጠለ የቶባኮ ቅጠል በውስጡ ኒኮቲን፣ ለካንሰር የሚዳርጉ ንጥረ ነገሮችና እንዲሁም ሌሎች ለድድና ለአፍ ካንሰር የሚያጋልጡ፣ መርዛማ ኬሚካሎች ሲኖረው፣ በሚቀጣጠልባቸው ወቅት በጭስ መልክ ወደ ሳንባችን የሚላከው የኬሚካሎች ጥርቅም ከላይ ከተጠቀሱት በተጨማሪ ካርቦን ሞኖኦክሳይድ እንዲሁም ሌሎች ከ4000 በላይ የሆኑ የተለያዩ ኬሚካሎች በተለያየ መልኩ ይኖረዋል፡፡ በመሰረቱ ባደጉ ሀገሮች ውስጥ በአሁኑ ጊዜ የሲጋራ አጫሾች ቁጥር እየቀነሰ ባለበት ዘመን በሀገራችን ደግሞ የሲጋራ አጫሽ ቁጥር መጨመሩ ሳይስተዋል አይታለፍም፡፡ የሲጋራ ሱስን በተመለከተ የተደረጉ የተለያዩ ጥናቶች ሲኖሩ አንዳንድ ጥናቶች እንደሚያመላክቱት ለሲጋራ ሱስ እንድንጋለጥ ሊያደርጉ የሚችሉ የተለያዩ የሰውነት ጂኖች ሲኖሩ እነዚህም አንዳንዶቹ በሰውነት ውስጥ የገባውን የኒኮቲን መጠን ተጣርቶ የመውጣቱን ሂደት የሚያስተጓጉሉ ሲሆኑ ሌሎች አይነቶች ደግሞ አንድ ሰው ሱሰኛ የመሆን ዕድል እንዲኖረው የሚያጋልጡ የጂን አይነቶች ናቸው፡፡ ከዚህም እንደምንረዳው አንድ ቤተሰብ ውስጥ የሲጋራ ሱሰኛ ያለ እንደሆነ በተመሳሳይ ቤተሰብ ውስጥ የሲጋራ አጫሽ የመኖር እድሉ ከፍተኛ መሆኑ ነው፡፡ ይህንን ስንል ግን በመሰረቱ በዘር የመተላለፍ ሁኔታው ለዚህ ምክንያት ሊሆኑ የሚችሉ የተለያዩ ጂኖች መኖራቸውን እንደሚያመላክተው ሁሉ፣ በአንፃሩም ደግሞ የማህበረሰባዊ ግንኙነት እና ሌሎች የሚያደርጉትን አዲስ ነገር ከመሞከርና ከመልመድ ጋርም ተያይዞ ሊታይ ይችላል፡፡ በዚህም ሳቢያ የተሻለ ስለሱስ ግንዛቤ ሊሰጡን የሚችሉ ጥናቶች አሁንም እየተካሄዱ ነው፡፡

ሲጋራ ማጨስ ሊያስከትላቸው የሚችላቸው ችግሮች

በሀገራችን ያለው የሲጋራ አጫሽ ቁጥርና በሲጋራ ሳቢያ የሚሞተው የሰው ቁጥር በውል ባይታወቅም በአሜሪካ ውስጥ በአንድ ዓመት ውስጥ ከ400,000 በላይ ሰዎች በሲጋራ ምክንያት ካለ ዕድሜያቸው ለተለያየ ችግርና ብሎም ለሞት ይጋለጣሉ፡፡ ሲጋራ ከሚያጨሱ ሰዎች ውስጥም 40 በመቶ የሚሆኑት ሲጋራ ማጨስ ያላቆሙ እንደሆነ በአፍላ ዕድሜ ለሞት ይጋለጣሉ፡፡

በሲጋራ ሳቢያ የሚመጡ ችግሮች እንደሚጨሰው የሲጋራ ብዛትና ጊዜ ይወስን እንጂ በጥቅሉ ግን ማንኛውም የሲጋራ አጫሽ ከዚህ በታች ለተዘረዘሩት ችግሮች ሲጋራ ከማያጨሱ ሰዎች ይልቅ የተጋለጡ ናቸው፡፡

- የአተነፋፈስ መስመር ችግሮች /Respiratory system/፡- የሲጋራ ጭስ በዋነኝነት የሚገባውና ተጣርቶ የሚወጣው በሳንባ እንደመሆኑ መጠን በአተነፋፈስ መስመሮች ላይ የሚደርሰው ጊዜያዊም ሆነ ቀጣይነት ያለው ችግር በርካታ ነው፡፡ ነገር ግን አንድ ሰው ሲጋራ ማጨስ ባቆመ ከ1-2 ዓመት ባለው ጊዜ ውስጥ ሁሉም ነገር ከነጭራሹ ወደ ነበረው ይመለሳል ማለት ባይቻልም ከዛ ብዙ የማይተናነስ ለውጥ ይታያል፡፡

- የልብና የደም ስሮች ችግሮች /Cardiovascular sysetem/፡- የሲጋራ አጫሾች ለልብ ድካምና ለተለያዩ የልባና የደም ስር ችግሮች የበለጠ የተጋለጡ ሲሆኑ በተለይ ደግሞ የደም ግፊት፣ የስኳር ህመምና ከፍተኛ የሰውነት ቅባት መጠን ያለባቸው ሰዎች ላይ ይህ ችግር ገኖ ይታያል፡፡ አንድ ሰው ሲጋራ ማጨስ ካቆመ በኋላ ግን እነዚህ የተለያዩ ችግሮች በተወሰነ መልኩ የመከሰት ዕድላቸው ይቀንስና ከ15 ዓመታት በኋላ ሲጋራ አጭሶ ከማያውቅ እኩል የመሆን ዕድል ሊኖረው ይችላል፡፡

- ካንሰር፡- በሲጋራ ሳቢያ ሊከተሉ የሚችሉ የካንሰር አይነቶች እጅግ በርካታ ሲሆኑ እነዚህም የአፍ፣ የላይኛው የትንፋሽ ቧንቧ፣ የሳንባ የምግብ ቧንቧ፣ የጣፍያ፣ የኩላሊት፣ እንዲሁም የሽንት ፊኛ ካንሰር በዋነኛነት ይጠቀሳሉ፡፡ ከዚህም በተጨማሪ የማህፀን በር ካንሰርና የጨጓራ ካንሰር የመከሰት ዕድሉ ከፍተኛ መሆኑን የሚያመላክቱ በርካታ ጥናቶች አሉ፡፡ ሲጋራ ማጨስ ማቆምን ከመቀጠል ይልቅ ለካንሰር የመጋለጥ እድልን እጅግ ይቀንስ እንጂ ከ20 ዓመት በላይ ሲጋራ ማጨስ ባቆሙ ሰዎች ላይ ራሱ ሲጋራ አጭሰው ከማያውቁ ሰዎች ይልቅ ለካንሰር የመጋለጥ ዕድላቸው የጨመረ ነው፡፡
- እርግዝና ላይ የሚያመጣው ችግር፡- ሲጋራ የሚያጨሱ ሴቶች በእርግዝና ወቅት ምንም ሲጋራ ባያጨሱ በእርግዝናው ወቅት በፅንሱ ላይ የሚታይ ችግር የለም ማለት ይቻላል፣ ነገር ግን በእርግዝና ወቅት ሲጋራ ማጨስ ለተለያዩ ከማስወረድ እስከ ቀድሞ ካለጊዜው ምጥ መምጣት የሚደርስ የእርግዝና ችግር ከማስከተሉም በላይ በተጨማሪ በጽንሱ ላይ የሚያስከትለው ችግር ከአዕምሮ ዘገምተኝነት እስከ ሞት ድረስ ሊሆን ይችላል፡፡ ከተወለደም በኋላ አካላዊ የሆነ የተዛባ አፈጣጠር ይዞ የማደግ ዕድል ሊኖረው ይችላል፡፡

- ከላይ የተጠቀሱት ችግሮች ዋና ዋና ይሁኑ እንጂ በተጨማሪም ደግሞ የጨጓራ ቁስለት፣ የአጥንት መሽከርከርና መሳሳት፣ የአይን ሞራ፣ ከጊዜው ቀድሞ ማረጥ፣ የቆዳ መሸብሸብና መጨማደድ፣ በሴቶች ላይ የሐሞት ጠጠር እንዲሁም በወንዶች ላይ ደግሞ ስንፈተ ወሲብ ሊያስከትል ይችላል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ የአካባቢ ብክለት እንደማስከተሉ መጠን በአካባቢው ያለውን ሰው በመበከል እነዚህ የሁለተኛ ደረጃ አጫሾች የተባሉት ከላይ ለተጠቀሱት ችግሮች በከፊልም ቢሆን እንደየሁኔታው የተጋለጡ ናቸው፡፡

በአጠቃላይ ስናየው ግን ሲጋራ ማጨስን ከነአካቴው አለመጀመርና አጠቃላይ አለማጨስ የተሻለው አማራጭ ሆኖ ሳለ ሲጋራ የሚያጨሰውም በራሱ ላይና በህብረተሰቡ ላይ ሊያስከትል የሚችለውን ችግር በማሰብ የተለያዩ መንገዶችን ተጠቅሞ ማቆም ተገቢ ነው፡፡ ጭስ በጨሰበት የሚታይ እሳት ብቻ ሳይሆን ልክ እንደ ሲጋራው ብዙም ሳይታይ የሚያቃጥል ብሎም የሚያጠፋ እሳት አለውና ህይወት ማጥፋቱን እያወቅን ከሲጋራ የጥፋት እሳትና የድብብቆሽ ሱስ የማርካት ፍላጎት ልንርቅ ይገባል፡፡


በጋምቤላ ክልል ጎደሬ ልዩ ስሙ ዱንቻ አማርኛ ተናጋሪ ዜጎች ተፈናቀሉ ‪

$
0
0

(ምንሊክ ሳልሳዊ)

በጋምቤላ ክልል ከቴፒ ከተማ ወጣ ብሎ በሚገኘው ጎደሬ ልዩ ስሙ ዳንቻ ተብሎ በሚጠራው አከባቢ የሚኖሩ እና በተለያየ ስራ ላይ ተሰማርተው የሚገኙ አማርኛ ተናጋሪ ኢዮጵያውያንን ከሃገራችን ውጡልም በማለት ማፈናቀል መጀመሩን ከአከባቢው የደረሱን መረጃዎች ይጠቁማሉ።
news
ከሶስት ቀን በፊት በለሰለሰ መልኩ የተጀመረው እና በመዠንገር የወያኔ ቅጥረኛ ካድሬዎች የሚመራው የማፈናቀል ድርጊት በአሁኑ ወቅት ወደ ግጭት ተለውጦ ሃይልን በመጠቀም ላይ ሲሆኑ ከአከባቢው የሚኖሩ ውጡ የተባሉ አባወራዎች ቤተሰቦቻቸውን ይዘው ንብረቶቻቸውን በመተው ወደ ቴፒ ከተማ እየተሰደዱ መሆኑን ታውቋል።

በዛሬው እለት የአማርኛ ተናጋሪ ዜጎችን መኖሪያ በ እሳት በመለኮስ ያቃጠሉ ሲሆን በአከባቢው የሚሰጠው የሚኒስትሪ ፈተና መቋረጡን ምንጮቹ አክለው ገልጸዋል። ትምህርት ቤቶችን እና የመንግስት መስሪያቤቶች የተዘጉ ሲሆን በ3 ኦራል መኪኖች መጥቶ ከተማው እና ገጠራማ አከባቢዎች ላይ የፈሰሰው የወያኔ የጦር ሰራዊት ግጭቱን ከማባበስ ውጪ ምንም አይነት መረጋጋት ሊፈጥር ያልቻለ ሲሆን ወታደሮችን ባዩ ጊዜ የአከባቢው ካድሬዎች =ጭራሽ ብሶባቸው ዜጎችን ሲያሳድዱ ተስተውሏል። ሲሉ ምንጮቹ የላኩልን መረጃ ይጠቁማል።

በሐረር የተገኘ የጅምላ መቃብር ጥያቄ አስነሳ

$
0
0

Haraer ethiopiaበሐረሪ ክልል ሐረር ከተማ አቅራቢያ በሚገኘው ሐማሬሳ ቀበሌ ውስጥ ሰሞኑን በተገኘ የጅምላ መቃብር ምክንያት አንዳንድ የከተማው ነዋሪዎች ጥያቄ ማንሳታቸውን ምንጮች ለሪፖርተር ገለጹ፡፡

ሰሞኑን አካባቢው ለጥቃቅንና አነስተኛ ተደራጆች ሼድ መሥሪያ ሲቆፈር በጅምላ የተቀበሩ ሰዎች አፅም መገኘቱን የጠቆሙት ምንጮች፣ የከተማው አስተዳደር ቁፋሮ እንዲቆም ቢያዝም፣ አንዳንድ ነዋሪዎች ሙሉ በሙሉ መቆፈር እንዳለበትና በጅምላ የተቀበሩት ዜጎች ቁጥር መታወቅ እንዳለበት በመግለጽ ተቃውሞ ማቅረባቸውን ተናግረዋል፡፡

ቦታው በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዘመነ መንግሥት የሦስተኛው ክፍለ ጦር መቀመጫ እንደነበርና በደርግ ዘመነ መንግሥትም የጦር ካምፕ ሆኖ መቀጠሉ ታውቋል፡፡

ምንጮች እንደሚሉት በተለይ በደርግ ዘመነ መንግሥት በርካታ ወጣቶችና የአካባቢው ነዋሪዎች ተገድለው በጅምላ ተቀብረዋል፡፡ ኢሕአዴግ አገሪቱን እንደተቆጣጠረ በተለያዩ አካባቢዎች በጅምላ የተቀበሩ ዜጎች አስከሬንን ማስወጣቱ ይታወሳል፡፡ በሐረር ከተማም በዘመኑ በሰዎች ላይ ግድያ በጅምላና በተናጠል የተፈጸመ ቢሆንም፣ የተቀበሩበት ቦታ አለመታወቁና ጠቋሚ በመጥፋቱ እስካሁን ድረስ አስከሬኖች ሳይገኙ መቆየታቸውን ምንጮች አስረድተዋል፡፡

ኢትዮጵያን ለ17 ዓመታት ሲመሩ የነበሩት ሌተና ኮሎኔል መንግሥቱ ኃይለ ማርያምም፣ አሁን የጅምላ መቃብሩ በተገኘበት ቦታ ላይ የነበረው የሦስተኛው ክፍለ ጦር አባል እንደነበሩ የገለጹት ምንጮች፣ ሥልጣን ከያዙ በኋላ ተቃውሞ ባደረጉ የኢትዮጵያ ወጣቶችና የወቅቱን ሥርዓት ተቃዋሚዎች ላይ የተፈጸመው ጭፍጨፋ ሁሉንም የአገሪቱን ክልሎች ያዳረሰ ለመሆኑ፣ የሐረሩ የጅምላ መቃብር መገኘት ማጠናከሪያ ማስረጃ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

በሐረር በተገኘው የጅምላ መቃብር ምክንያት በወቅቱ ለተሰው ዜጎች ማስታወሻ እንዲሆን ሐውልት ሊቆም እንደሚገባ አንዳንድ ነዋሪዎች የከተማ አስተዳደሩን መጠየቃቸውን ምንጮች ጠቁመዋል፡፡

በሐረሪ ክልል ሐረር ከተማ አካባቢ ተገኘ ስለተባለው የጅምላ መቃብርና አንዳንድ ነዋሪዎች አንስተዋል ስለተባለው ተቃውሞ ማብራሪያ እንዲሰጥ የክልሉ መስተዳደር ለመጠየቅ ቢሞከርም ምላሽ ማግኘት አልተቻለም፡፡ ነገር ግን አንዳንድ ስማቸው እንዲጠቀስ ያልፈለጉ የክልሉ ከፍተኛ ባለሥልጣናት እንደገለጹት፣ የጅምላ መቃብር መገኘቱ እውነት ነው፡፡ የተገኘውም ቦታውን ለጥቃቅንና ለአነስተኛ ተደራጆች ሼድ ሠርቶ ለመስጠት ቁፋሮ ሲደረግ መሆኑን አረጋግጠው፣ አንዳንድ የግል አጀንዳቸውን ለማራመድ ሰበብ የሚፈልጉ ግለሰቦች ሕዝቡን ከለላ አድርገው ለመንቀሳቀስ ሞክረዋል ብለዋል፡፡ ሕዝቡ ሊተባበራቸው ባለመቻሉ አፍረው እንቅስቃሴያቸውን ማቆማቸውንም አስረድተዋል፡፡ ቁፋሮውም እንዲቆም ተደርጎ የክልሉ መንግሥት እየተነጋገረበት መሆኑን አስረድተዋል፡፡

Source: Ethiopian Reporter

የትግራይ ብሄርተኝነት እንዴት ወደ ፋሽስት ስርዓትነት እያመራ እንደሆነ ለማሳየት እንሞክር(ክፍል 1) (ዶ/ር አሰፋ ነጋሽ)

$
0
0

የትግራይ ብሄርተኝነት እንዴት ወደ ፋሽስት ስርዓትነት እያመራ እንደሆነ ለማሳየት እንሞክር(ክፍል 1)
(ዶ/ር አሰፋ ነጋሽ)tgh

የሰው ልጆች አብረው በማህበረሰብ ለመኖር ይቻላቸው ዘንድ ለአብሮ መኖር ፀር የሆኑ ምግባሮችንና ባህሪዎችን ማስቀረት መቻል አለባቸው። አለበለዚያ ማህበራዊ ኑሮ ሊታሰብ አይችልም። ሰውን ከእንሰሳየሚለየው ከስሜት ባሻገር የማሰብና የማመዛዘን ክህሎቱ ነው። ህሊና አንድ ሰው በጎና ክፉውን፤ መጥፎና ጥሩውን፤ ትክክለኛና ሃሰተኛውን ነገር ለይቶ እንዲያውቅ የሚያስችለውን ችሎታ ወይም ክህሎት አመልካች ነው። የሰው ልጅ የማሰብና የማሰላሰል ልዩ ችሎታ ስላለው በሚኖርበት ማህበራዊ ስፍራ የሚከሰቱትን ነገሮች ሊገነዘብና ሊዳኝ ይችላል። ልጅ ሲያድግ በጎውና ክፉውን እየለየ የሚያውቀው ከአሳዳጊ ቤተሰቦቹ፣ ከጎረቤቱ፣ በሚኖርበት አካባቢ ከሚገኙ ሰዎች፣ ተቇሞች፣ ትምህርት ቤት፣ መስጊድ፣ ቤተ ክርስቲያን ወዘተ ነው። የህሊና ዳኝነትና ለሱ መገዛት መቻል የአንድን ሰው ነፃ መሆንና በራሱ ነፃነት በጎናክፉውን የመወሰን ችሎታን ያሳያል። በጎሳ ብሄርተኝነት የተለከፈ አንድ ሰው አንደ ራስ-በቅ(self reliant) ሰው በራሱ ሀሳብና ፈቃድ ተመርቶ ማህበራዊ ህይወቱን ሊመራ አይችልም። በዚህ አይነት በጎሳ ብሄርተኝነት አይምሮአቸው የተመረዙ ሰዎች የግል ማንነታቸው መገለጫ የሆነውን እንደ ሰው የማሰብ ችሎታቸውን ለጎሳ መሪዎቻቸው አሳልፈው ስለሚሰጡ የአንድ በጎሳ ብሄርተኝነት አስተሳሰብ የተመረዙ ሰዎች በሙሉ የጎሳ መሪዎቻቸው የሚነግሯቸውን እየሰሙና እየተከተሉ እንደ አንድ ሰው ወይም እንደ ጎሳ መሪያቸው ማሰብ ይጀምራሉ። ይህ ፈረንጆች “group thinking” የሚሉትና የአንድ አክራሪ የጎሳ ድርጅት ተከታዮች አንድ ወጥ የሆነ አስተሳሰብ (homogenization of thought) ተሸካሚዎች የሚሆኑበት ሂደት ነው። በዚህ ምክንያት በአክራሪ የጎሳ አስተሳሰብ የተመረዙ ሰዎች በጎሳ መሪዎቻቸው ትዕዛዝ(ውሳኔ) ህይወታቸውን እንዲመሩ ይደረጋል። የጎሳ መሪዎቹ የወደዱትን ይወዳሉ የጠሉትን ይጠላሉ። የጎሳ መሪዎቹ የመረጡለትን ነገር ሁሉ አንድ ሰው ለመቀበል ይገደዳል። ምን እንደሚያስብ ፤ ከማን ጋር ቡና መጣጣት እንዳለበት፤ ከማን ጋር መወያየት፤ ማንን ማፍቀር ማንን መጥላት፤ በየትኛው የፖለቲካ ስብሰባ ላይ መሳተፍ ወይም አለመሳተፍ እንደሚገባው ወዘተ የጎሳ መሪዎቹ ይነግሩታል። በዚህ አይነት የግል ማንነቱን ያጣ ሰው ይሆናል። በአለም ላይ ሰዎች የጎሳ ብሄርተኝነትን፣ አክራሪ የሃይማኖት ፍልስፍናን ወዘተ በመሣሠሉ መርዘኛ አመለካከቶችን በሚያራምዱ ፍልስፍናዎች ምክንያት የህሊና ዳኝነት ችሎታቸውንም ሆነ ክህሎታቸውን አሽቀንጥረው የጣሉበት ሁኔታ እንደነበረ ታሪክ ዘግቧል። ለምሳሌ በናዚ ጀርመን ውስጥ ሰዎች እንደ ሰው ለህሊናቸው መገዛትን አቁመው ህሊና ቢስ በመሆን በጥላቻ የሰከሩ መሪዎቻቸውን እነ ሂትለርን፤ በጣሊያን እነ ሞሶሎኒን በጭፍን የተከተሉበት ሁኔታ እንደነበር በ ሁለተኛው የአለም ጦርነት ወቅት አይተናል። በዚህ ወቅት በናዚ ፍልስፍና መስፋፋት የተነሳ ብዙ ጀርመኖች ህሊናቸውን ስተው የሂትለር ፖርቲ ደጋፊና አጫፋሪ ሆነው ስለነበር ከብዛኞቹ የጀርመን ተወላጆች ሰው የሚያሰኛቸውን የህሊና ዳኝነት ክህሎት አሽቀንጥረው በመጣል የግል ማንነታቸውን አጥተው የናዚን ፋሽስት የፖለቲካ ፍልስፍና ስርዓት ተከታዮችና አቃፊ ደጋፊዎች ሆነው ነበር። የናዚም ሆነ የፋሽስት አክራሪ የጎሳ ብሄርተኝነት ተከታዮችን ከሰውነት ተራ በመውጣት የግለሰብ ማንነታቸውን አጥፍቶ እንደ እንሰሳት መንጋ የአንድን የጎሳ ድርጅት መሪዎች በጭፍን እንዲከተሉ ያደርጋል። እነዚህ በመሪዎቻቸው ሀሳብና ትዕዛዝ በጭፍን የሚመሩ ህሊና ቢስ የተደረጉ በጎሳ ብሄርተኝነት ስሜት የሰከሩ የአንድ ጎሳ ተወላጆች የሆኑ ጀሌዎች መሪዎቻቸው አድርጉ ያሏቸውን ነገሮች ሁሉ ካለ አንዳች ማወላወልና ማንገራገር ይፈፅማሉ። በዚህ አይነት ህሊናቸውን ያጡ ጀሌዎች በበዙበትና ስልጣን በተቆናጠጡበት ሃገር ውስጥ ሊከሰት የሚችለው አደጋ የብዙ ንፁሃን ዜጎችን ህይወት ሊቀጥፍ ይችላል፤ ሀገርን ያፈርሳል፤ ህዝብን ይበትናል። ትላንት የናዚ ጀርመኖች ፍልስፍና ገዥና ዋና አስተሳሰብ (dominant ideology) በነበረበት ግዜ በሚሊዮን የሚቆጠሩ አይሁዳዊያን፣ እስላሞች፣ ጂፕሲዎች ወዘተ በገፍ እየተነዱ ሲፈጁ አብዛኛው የጀርመን ህዝብ ድርጊቱን ሳይቃወም እንዲያውም ሲደግፍ ታይቶ ነበር። በዛን ጊዜ በርካታ ጀርመናዊ በናዚ ጭፍን የጀርመን የበላይነት ፍልስፍና ( Deutschland ueber alles) ወይም ጀርመን ከሁሉ በላይ በሚለው የአርያን የዘር የበላይነት በሚያንፀባርቅ አስተሳሰብ አይምሮው ተመርዞ ነበር። በዚህ ምክንያት የጀርመን ህዝብ በጎውና መጥፎውን የሚለይበትን ህሊናውን አሽቀንጥሮ በመጣል የራሱን ማንነት አሳልፎ ለናዚ መሪዎች በገፀ-በረከትነት ሰጠ።
ዛሬ በኢትዮጲያችን ተመሣሣይ ሁኔታ እየታየ ነው ብዬ እሞግታለሁ። የወያኔ ድርጅት ትግል ሲጀመር የዚህን ድርጅት እኩይ አላማ በመቃዎም የተገረፉ፣ የተገደሉ፣ የተሰደዱ የትግራይ ተወላጆች እንዳሉና ለነዚህም ከፍተኛ አክብሮት እንዳለኝ ልገልፅ እፈልጋለሁ። ለሀገራቸው ያደረጉትንም ውለታ አልረሳም። ይሁን እንጂ ለ 17 አመታት በጦርነት እንዲሁም ላለፉት 38 አመታት ወይም 39 አመታት በፀረ ኢትዮጲያ የጥላቻ ፕሮፓጋንዳ ውስጥ አብዛኛው የትግራይ ተወላጅ በተለይም ቀለም ቆጠረ የሚባለው ክፍል በዛሬው ወቅት የመርዘኛው የትግራይ ብሄርተኝነት ሰለባ በመሆን የዚህ ያለው ፀረ ኢትዮጵያ የሆነ የወያኔ አገዛዝ ደጋፊና አቃፊ ከሆነ ውሎ አድሯል። በዚህ ምክንያት የወያኔ ስርዓት በሌሎች የኢትዮጲያ ጎሳዎች ላይ የሚፈፅመውን ግፍ ከመቃወም ይልቅ በርካታ የትግራይ ተወላጅ ይህንን የወያኔን ስርዓት በፅናት ከሚቃወሙ ኢትዮጲያውያን በተቃራኒ ጎን መቆምን መርጧል። ይህንን ገደምም ጠመምም ሳላደርግ ባለፉት 21 አመታት ስናገር እንደቆየሁት ዛሬም በናንተ ፊት በአደባባይ እናገራለሁኝ። የዚህንም አደገኛ አዝማሚያ አውዳሚ ፍፃሜ አመለክታለሁኝ። እስቲ በቅድሚያ የቀድሞ የወያኔ ትግሬዎች መሪ መለስ ዜናዊ ለትግራይ ህዝብ ካደረገው እጅግ እብሪትና የማን አለብኝነት ከተጠናወተው ንግግሩ አንዱን ጠቅሼ የትግራይ ብሄርተኝነት ከምን አደገኛና ወደ ሗላ ሊመለስ ከማይችልበት ጫፍ እንደደረሰ መስረጃ አቅርቤ ላስረዳ ልሞግት። ይህ ከዚህ በታች የምጠቅስላችሁ ንግግር መለስ ዜናዊ መቀሌ ውስጥ የወያኔን የድል በዓል ሲያከብር በመቶ ሺዎች ለሚቆጠር የትግራይ ህዝብ ካደረገው ንግግር ነው፦

“ይህ ህዝብ እንኯን የሌሎች ባዕዶች ያልሆነ። እንኯን ከእናንተ ተፈጠርን። ይህ የእያንዳንዱ ታጋይ እምነት ነው። እንኯን ከእናንተው ማህፀን ተፈጠርን። እንኯን የኛ ሆናችሁ። እንኯን የሌላ የባዳ አልሆናችሁ። እንኯን በማዶ እያየናችሁ የምንቀናባችሁ አልሆናችሁ።”

በዛው እለት በተያያዘ ንግግሩ መለስ ለትግራይ ወጣቶች እንዲህ ብሎ መልዕክቱን አስተላልፎ ነበር፦

“እናንት ወጣቶች እዚህ ያላችሁበት መድረክ እንድትደርሱ ሲባል ታላላቆቻችሁ ላባቸውንና ደማቸውን አፍስሰዋል። ታላላቆቻችሁ በየጉራንጉሩ በየሸለቆውና በየተራራው ቀርተዋል። ታላላቆቻችሁ አጥንታቸው በየተራራው ተበትኗል። አጥንቶቻቸው በየተራራው የተበተነበት ምክንያት ትግራይ እንድትለማ በሚል ነው። እነኚህን አጥንቶች እንዳትረግጧቸው እንዳታረክሷቸው፤ ሁኔታውን ካመቻቹላችሁ በሗላ እንዳትከዷቸው ሌት ተቀን መጣር ይኖርባችሗል። “

ይህ ንግግር አንድ በብሄርተኝነት የሰከረ እነ ሂትለር ካደረጏቸው የእብሪት ንግግሮች የላቀ ነው።ዛሬ በዚህ የተቀሰቀሱ ልባቸው ያበጠ በሚሊዮን የሚቆጠሩ የትግራይ ተወላጆች ተፈጥረዋል።
ዛሬ የወያኔ ትግሬዎችና በስራቸው ያሰለፏቸው የጎሳ ተከታዮቻቸው በአብዛኛው ህሊና እንዳለው ግለሰብ በጎውንና ክፉውን አመዛዝኖ ፍርድ ከመስጠት ይልቅ በወያኔ ድርጅት ትዕዛዝ እንደ መንጋ በጀሌነት የሚመሩ ፍጡራን ሆነዋል። የአንድ ጎሳ ተወላጆች የራሳቸው ጎሳ ተወላጆች የሆኑ ሰዎች በሌሎች ከነሱ ጎሳ ውጪ ባሉ ተወላጆች ላይ የሚፈፀሙትን ማናቸውንም ህሊና ያለው ሰው ማየት የሚችለውን ጥፋትና ግፍ ለማየት ይሳናቸውና የጎሳ መሪዎቻቸው የሚሏቸውን እየሰሙ ይህን ግፍ ለሚፈፅሙት የጎሳ መሪዎቻቸው ጭፍን ድጋፋቸውን ሲሰጡ ይህ ሁኔታ ለአንድ ሃገር ታላቅ አደጋን ይጋብዛል። የጎሳ ፍጅት (Genocide) መነሾም ይሆናል። በብዙ መቶ ሺህ የሚቆጠሩ የታጠቁ የትግራይ ተወላጆች በሃይል ከጎንደር ተቆርሶ ወደ ትግራይ ክልል የተጠቃለለውን ለም መሬት ይዘው አሻፈረኝ ያለውን ነባሩን ህዝብ ገድለው ከፊሉን የተወለደበትንና ያደገበትን ቀዬ ጥሎ ወደ ሱዳን ፣ አዲስ አበባና ጎንደር እንዲሰደድ ማድረጋቸው የወያኔ ትግሬዎች የተፀናወታቸውን ህሊና ቢስነትና አመለካከታቸው በጎሳ አስተሳሰብ የተመረዘበትን ሁኔታ ቁልጭ አድርጎ ያሳያል። በቅርቡም የወያኔ ትግሬዎች መንግስት ታሪካዊውን የዋልድባን ገዳም የትግራይ ክልል አካል ነው በማለት በገዳሙ ውስጥ የነበሩትን የትግራይ ቀሳውስትና መነኮሳት በጎሳ ስሜት ቀስቅሶ ከጎኑ በማሰለፍ የወሰደው ገዳሙን የመቆጣጠር እርምጃ ይህንኑ ህሊና ቢስነትና የአንድ አናሳ የጎሳ ተወላጆችን እብሪት የሚያሳይ ድርጊት ነው። እንደ ኢትዮጲያ ግፍ ሞልቶ በፈሰሰበት ሀገር ውስጥ ይህ አይነቱ ጭፍንነት ሗላ ጎሳን መሠረት ላደረገ ከፍተኛ ፍጅት(Genocide) የሚዳርግ ነው። ዛሬ የአማራን ህዝብ ከሶማሌ ከቤኒሻንጉል ከደቡብና ከኦሮሚያ ክልል እንዲዎጡ የተደረገበት በፋሽስቱ የጣሊያን የወረራ ግዜ እንኯን ያልተፈፀመ ዘግናኝ ድርጊት ሲፈፀም የዚህን የአማራ የጎሳ ጥቃት እያስፈፀሙ ያሉት የወያኔ ትግሬዎች መንግስት፣ የወያኔ ትግሬዎች መንግስት ከላይ እስከታች የዘረጋው የስለላ መረብ አዛዦችና የወታደራዊ ጭፍሮቻቸው እንደሆኑ አንዘንጋ። ~ ~

በክፍል ሁለት የወያኔ መንግስት አንዳንድ ፋሽስታዊ ጠባዮችን እንመለከታለን።

በአዲስ አበባ የመሬት አስተዳደር ቢሮና በሌሎች ተቋማት ላይ ፓርላማ ዕርምጃ እንዲወስድ ተጠየቀ

$
0
0

ዋና የሕዝብ እንባ ጠባቂ ተቋም ለሕዝብ አቤቱታ መፍትሔ የማይሰጡ ያላቸውን ተቋማት ፓርላማው ዕርምጃ እንዲወስድባቸው አሳሰበ፡፡ ከእነዚህ ተቋማት መካከል የአዲስ አበባ ከተማ የመሬት ልማትና አስተዳደር ቢሮ፣ እንዲሁም ሌሎች  የከተማው ተቋማት ከፍተኛውን ድርሻ ይዘዋል፡፡

addis-ababa-realethiopia-141ዋና የሕዝብ ዕንባ ጠባቂዋ ወ/ሮ ፎዚያ አሜን የአሥር ወራት የሥራ አፈጻጸም ሪፖርታቸውን ሰኔ 3 ቀን 2006 ዓ.ም. ሲያቀርቡ፣ ተቋሙ በምርምራ ውጤት ላይ ተመሥርቶ የተሠሩ ጥፋቶች እንዲታረሙና በደል የደረሰባቸው መፍትሔ እንዲያገኙ በማድረግ ላይ እንደሚገኝ አስታውቀዋል፡፡

የሕዝብ እንባ ጠባቂ ተቋም የሥራ ኃላፊዎች ከክልሎች፣ ከአዲስ አበባ ከተማ  አስተዳደርና ከድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ጋር በመነጋገር፣ አብዛኞቹ ፈጻሚ መሥሪያ ቤቶች የሚቀርቡባቸውን አቤቱታዎች እንዲያርሙና የተበደሉ ደግሞ መፍትሔ እንዲያገኙ ማድረግ መቻሉን በበጐ ጐኑ አንስተዋል፡፡

ይሁን እንጂ አንዳንድ የመንግሥት አስፈጻሚ መሥሪያ ቤቶች የሕዝብ እንባ ጠባቂ ተቋም በምርምራ ላይ ተመሥርቶ የሚያቀርብላቸውን የመፍትሔ ሐሳብ ተግባራዊ ካለማድረጋቸውም በላይ፣ የማይተገብሩበትን ምክንያት እንኳን አይገልጹም ብለዋል፡፡ በዚህም ምክንያት የሕዝብ ተዋካዮች ምክር ቤት የሕግና የአስተዳደር ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በልዩ ሁኔታ እንዲከታተላቸው ዝርዝር ሪፖርት እንደተላከለትና ኮሚቴውም በአሁኑ ወቅት አስፈላጊውን ሥራ በመሥራት ላይ እንደሚገኝ ጠቁመዋል፡፡

በዝርዝር ሪፖርት ለቋሚ ኮሚቴው ከተላለፉ ተቋማት መካከል የአዲስ አበባ አስተዳደር የመሬት ልማትና አስተዳደር ቢሮ፣ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሲቪል ሰርቪስ ኤጀንሲ፣ የአዲስ አበባ መንገዶች ባለሥልጣን፣ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የአራዳ ክፍለ ከተማ የመሬት ልማትና አስተዳደር ጽሕፈት ቤት ይገኙበታል፡፡

ከአዲስ አበባ ውጪ የተጠቀሱት ተቋማት የሐዋሳ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ጽሕፈት ቤት፣ የኢትዮጵያ ሶማሌ ክልል የእንስሳት ሰብልና ገጠር ልማት ቢሮ፣ የሐረር ክልል ፍትሕና ፀጥታ ጉዳይ ቢሮ ናቸው፡፡

የሕዝብ እንባ ጠባቂ ተቋም በአሥር ወራት ጊዜ ውስጥ 2,948 የአቤቱታ መዝገቦች የቀረቡለት መሆኑን የገለጹት ዋና እንባ ጠባቂ ወ/ሮ ፎዚያ፣ መዝገቦቹ በአጠቃላይ 17,682 አቤቱታ አቅራቢዎችን ይመለከታሉ ብለዋል፡፡

ቴዲ አፍሮ ኮካ ኮላ ባለፈው ሳምንት ላወጣው መግለጫ የሰጠው ምላሽ

$
0
0

አስከመጨረሻው የዓለም ዋንጫ መከፈቻ ዕለት የመጨረሻ ሴኮንድ ድረስ እንጠብቃለን፡፡

989TeddyAfro_NYC_26

 

አስከመጨረሻው የዓለም ዋንጫ መከፈቻ ዕለት የመጨረሻ ሴኮንድ ድረስ እንጠብቃለን፡፡

ሰኔ ግንቦት 23 2006 አለአግባብ እንዳይለቀቅ በተደረገው የዓለም ዋንጫ የኢትዮጵያው ቅጂ ሙዚቃ አስመልክቶ ያለንን አቋም በመግልፅ መግለጫ ማውጣታችን ይታወሳል፡፡
ምንም እንኳን መግለጫውን በድረ ገፃችን ላይ አትመን ለማውጣት ከመወሰናችን በፊት ጉዳዩን በተመለከተ ለኮካ ኮላ እና ወኪሉ ለሆነው ማንዳላ ቲቪ አስቀድመው እንዲያውቁት ብናደርግም እስከ አሁን ድረስ ምንም ዓይነት ምላሽ አላገኘንም፡፡ የዚህ ዓይነቱ ባህሪ ላለፉት በርካታ ወራቶች ተደጋግሞ ሳያቋርጥ የገጠመን በመሆኑ የሚያስደንቀን አልሆነም፡፡
እኛን ባስደነቀን መልኩ “ታዲያስ መጋዚን” በተሰኘ ድረ ገፅ ላይ ባለፈው ግንቦት 30 ቀን 2006 ዓ.ም ኮካ ኮላ ያወጣውን መግለጫ ለመመልከት የቻልን ሲሆን ምንም እንኳን ይህው መግለጫ በቀጥታ ለእኛ ያልደረሰን ቢሆንም ለክቡራን አድናቂዎቻችን በመግለጫው ውስጥ የተካተቱት ጭብጦች ምንም ዓይነት የውል፣ የፍሬ ነገር እና የህግ መሰረት የሌላቸው መሆኑን ማብራራቱ እና መግለፁ አግባብነት ይኖረዋል ብለን አምነናል፡፡
መግለጫው ቴዲ አፍሮ ከኮካ ኮላ ጋር እንዴት እና ለምን ግብ ግንኙነት እንዳደረገ እንደሚከተለው በማተት ይጀምራል፤ “ቴዲ አፍሮ አፍሪካ ባለው የኮካ ሰቱዲዬአችን የመጣው የኮካ ኮላ ቅጂ የሆነውን “ዓለም የኛ ነች” የተሰኘውን የፊፋ የዓለም ዋንጫ ሙዚቃ ልዩ ዓይነት የሆነውን ኢትዮጵያዊ ሙዚቃ ለማሰቀረፅ በታቀደ ግብ ነበር” ይላል መግለጫው፡፡
ይሁን እንጂ መግለጫው ማን “እንዳመጣው” እና ምርጫውንም እንዳደረገ አያመለክትም ወይም አይገልፅም፡፡ በመግለጫችን ላይ እንዳብራራነው ለኮካ ፕሮጄክት ወደ እኛ በመቅረብ ምርጫውን በማድረግ ተነሳሽነቱን የወሰደው አቶ ምስክር ሙሉጌታ ከመሆኑ በተጨማሪ ይህው ስው ከኮክ ሰቱዲዮ ጋር በማገናኘት ከኮካኮላ ማዕከላዊ፣ ምስራቅ እና ምዕራብ አፍሪካ ሊሚትድ ወኪል ከሆነው ከማንዳላ ቲቪ ጋር ውል እንድንዋዋል አድርጓል፡፡
ከአቶ ምስክር እና ከማንዳላ ቲቪ ጋር ኮካ ኮላ በቅደም ተከተል የአሰሪ እና ሰራተኛ እንዲሁም የወኪል እና የወካይ ግንኙነት ያለው ቢሆንም በመግለጫው ላይ አንዳችም ዓይነት ግንኙነት ስለመኖሩ ከማስተባበሉ አልፎ በመሄድ “ከቴዲ አፍሮ ጋር የተደረገው ውል ማንዳላ ሊሚትድ በተሰኘ እና መቀመጫው ናይሮቢ በሆነ አዘጋጅ ተቋም “በ3ኛ ወገን” በኩል የተፈፀመ ነው” በማለት በአፅንኦት ገልጾ ራሱን ከነበረው ትስስር ነጥሏል፡፡
3ኛ ወገን የሚለው ቃል …..የስምምነት ወይም የግብይት…. ወገን ያልሆነ እና አልፎ አልፎ ከስምምነቱ ወይም ከግብይቱ ውጪ የሆነ ወገን ተብሎ ይገለፃል፡፡ እንደ ኮካ ኮላ መግለጫ ከሆነ የኢትዮጵያ እና የኤርትራ የኮካ ኮላ ብራንድ ሥራ አስኪያጅ የሆኑት አቶ ምስክር ሙሉጌታ እና ለኮካ ኮላ በኮካ ስቱዲዮው በኩል ሙዚቃ ነክ ንብረቶችን ለማዘጋጀትና ለማስተዋወቅ የተለያዩ አገልግሎቶችን የሚያቀርብለት ወኪሉ ማንዳላ ቲቪ ኮካ ኮላ ከአደረገው ስምምነት እና ግብይት እንዲሁም በመግለጫው ላይ “የኮካ ሰቱዲዬአችን” በሚል ፍንትው ባለ አገላለፁ ካመለከተው ጋር አንዳችም ግንኙነት የሌላቸው ባይታወሮች ናቸው፡፡
አቶ ምስክር እንደ ተቀጣሪ ሰራተኝነታቸው እና ማንደላ ቲቪም እንደ ወኪልነቱ ልዩ ልዩ ሙዚቃ ነክ ንብረት አገልግሎቶች ለማከናወን በመዋዋል በማዕከላዊ፣ ምስራቅ እና ምዕራብ አፍሪካ ኮካ ኮላ ምትክ እና ፋንታ ህጋዊ ተግባራታቸውን ሲፈፅሙ ልክ ዋና መስሪያ ቤቱ አትላንታ ለሚገኘው እና መግለጫውን እንዳወጣው የኮካ ኮላ ተወካይ አንድ ዓይነት የሆነ የህግ ችሎታ/አቋም እና ውጤት አላቸው፡፡
ይህ በራሱ ተቀጣሪ ሰራተኛ እና በወኪሉ መካከል ያለውን የፍሬ ነገር እና የህግ ትስስር ሙሉ ለሙሉ በመካድ ኮካ ኮላ ባወጣው መግለጫው ላይ “ሶስተኛ ወገን” የሚል ከቶም አግባብነት በሌለው ቃል ተክቶ ራሱን ከማናቸውም ግንኙነት ለማራቅ ምክሯል፡፡ ይህም ሁኔታ በቅዱስ መፅሐፍ ላይ ጲላጦስ የፈፀመውን ፈፅሞ “ከደሙ ንፁህ ነኝ” ያለውን ጥቅስ ያስታውሰናል፡፡
ይህ ክብርን የሚያቃልል እና የሚነሳ መግለጫ የሰው ልጅን፣ የሁሉም አድናቂዎቻችንን እና የኮካ ኮላንም ደንበኞች ጭምር ዕውቀት፣ አእምሮ እና ግንዛቤ የሚገዳደር እና የሚፈታተን ነው፡፡ ይህም አድራጎቱ ቆሜለታለሁ ከሚለው የኩባኒያው የስነ ምግባር መርሆዎች ማለትም ከመልካም ስብእና፣ ታማኝነት፣ የህዝብ አመኔታ እና አሌኝታነት ጋር የሚፃረርም ነው፡፡
በእርግጥ ኮካ ኮላ ከቴዲ አፍሮ ጋር ማናቸውም ዓይነት ግንኙነት ከሌለው እንግዲያውስ በአጠቃላይ መግለጫውን ለማውጣትና ከሁሉም በላይ ደግሞ ቴዲ “ለአደረገው ጥረቱ ሙሉውን” የተከፈለው ስለመሆኑ እና “የተሰራው ሙዚቃ የማዕከላዊ፣ ምስራቅ እና ምዕራብ አፍሪካ ኮካኮላ ንብረት ሆኗል” በማለት አፅንኦት ሰጥቶ ለማረጋገጥ ለምን አሰፈለገው?”
አሳዛኙ ነገር ላለፉት ወራቶች ከኮካ ኮላ እና ከማንዳላ ቲቪ ጋር ስናደርግ በነበረው የቃል እና የፁሁፍ ግንኙነቶች ተመሳሳይና አስደንጋጭ ጎጂ ተግባራቶችን ስንቀበልና ስናስተናገድ ቆይተናል፡፡ እነኚህ ድርጊቶች ከቅን ልቦና የመነጩ ወይም የዕውቀት ማነሰ ውጤት ናቸው የሚል ዕምነት የለንም፡፡ ይልቁንም ሆን ተብሎ የሚፈፀም ፍፁም ተቋማዊ የማናለብኘነት አድራጎት ነው፡፡
ይህም ቢሆን ግን ራሱን በሚያከበር ኢትዮጵያዊ በሚመጥን ትዕግስት፣ ትህትና እና አክበሮት በጉጉት መለቀቁ እየተጠበቀ ያለውን ሙዚቃ ወይም ሊለቀቅ የማይችልበትን ምክኒያት አስከመጨረሻው የዓለም ዋንጫ መከፈቻ ዕለት የመጨረሻ ሴኮንድ ድረስ እንጠብቃለን፡፡

 

ቅድመ-ውህደቱና ልዩ ገጠመኞቹ

$
0
0

በ  ዘሪሁን ሙሉጌታ
ሰንደቅ

 

የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ) እና አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) የቅድመ ውህደት ስምምነት ሰኔ 1 ቀን 2006 ዓ.ም በመኢአድ ጽ/ቤት በተካሄደው የግማሽ ቀን ስነ-ስርዓት ተከናውኗል። በስነስርዓቱ ላይ በርካታ ታዋቂ ሰዎች፣ ፖለቲከኞች፣ የሚዲያ ባለሙያዎችና ዲፕሎማቶች ተገኝተው ነበር

የቅድመ-ውህደቱ አጠቃላይ ይዘት

Politiczedየውህደቱ የፊርማ ስነ-ስርዓት በተካሄደበት ወቅት የሁለቱ ፓርቲ አመራሮች ሰፋ ያለ ንግግር አድርገዋል። የሁለቱም መሪዎች ንግግር ውህደቱ ከመዘግየቱ በስተቀር አስፈላጊ መሆኑን አፅንኦት ሰጥተው ተናግረዋል። ከቅድመ ውህደት ስነ-ስርዓት ፊርማው በኋላ ለጋዜጠኞች አጠር ያለ ጋዜጣዊ መግለጫ ፕሮግራም ተዘጋጅቶ ስለነበር በፕሮግራሙ ላይ የተለያዩ ጋዜጠኞች ለሁለቱ ፓርቲ መሪዎች ጥያቄ አቅርበውላቸው ነበር።

ከቀረቡት ጥያቄዎች መካከል በቀጣይ በአንድ ወር ውስጥ ጠቅላላ ጉባኤ ተጠርቶ የሚመሰረተው ፓርቲ ስያሜ ምን ይሆናል የሚል ነበር። ለዚህ ጥያቄ ምላሽ የሰጡት ኢንጅነር ግዛቸው ሽፈራው ስያሜው የሁለቱን ፓርቲዎች ስያሜ ባቆራኘ መልኩ አዲስ ስም ይወጣል ብለዋል። ስያሜው የሚፀድቀው በአዲሱ ውህድ ፓርቲ ጠቅላላ ጉባኤ መሆኑንም አስረድተዋል።

በተመሳሳይ ሌሎች ፓርቲዎችን ታሳትፋላችሁ? ለሚለው የጋዜጠኞች ጥያቄ መኢአድና አንድነት በመዋቅር ጥንካሬና በአባላት ብዛት በአንፃራዊ ደረጃ ከሌሎች ፓርቲዎች የተሻሉ መሆናቸውን ጠቅሰው፤ ይህ ብቻ በቂ ባለመሆኑ ሌሎች ፓርቲዎች እንዲገቡበት በማድረግ ኢህአዴግን የሚፎከር አብይ ብሔራዊ ፓርቲ ለማቋቋም መታሰቡን ገልፀዋል። የአሁኑም የአንድነትና የመኢአድ ቅድመ-ውህደት እንደ ውህደት ማዕከል ሆኖ እንደሚያገለግል ያላቸውን ተስፋ ገልፀዋል።

በተጨማሪም በአንድ ወር ውጥ ጠቅላላ ጉባኤ ተጠርቶ አዲሱን ውህድ ፓርቲ ለመፍጠር የአቅም ጉዳይ በጋዜጠኞች ተነስቶ የነበረ ሲሆን፤ “ችግራችን የአመራር እና ድርጅታዊ አቅምን የማንቀሳቀስ እንጂ የአቅም አይደለም። አባላቶች በከፊልም ቢሆን የራሳቸውን ወጪ በመሸፈን ወደ አዲስ አበባ በመምጣት የሁላችንንም ፍላጎት እናሳካለን” ሲሉ ኢንጂነር ግዛቸው መልሰዋል። በቅርቡም የሁለቱም ፓርቲዎች ብሔራዊ ም/ቤት የጠቅላላ ጉባኤ አዘጋጅ በመሰየም ሁኔታውን ያፋጥናል ብለዋል። አዲሱ ውህድ ፓርቲም ከሁለቱ ፓርቲዎች የተውጣጣ 400 የጠቅላላ ጉባኤ አባላት ይኖሩታል ብለዋል።

ቀደም ሲል በመኢአድ በኩል “አንድነት ከመድረክ ካልወጣ ውህደቱ አይሳካም” የሚለውን ጥያቄ በተመለከተ ከጋዜጠኞች ለተነሳው ጥያቄ ጉዳዩ በሕግ ባለሙያዎች ታይቶ በመድረክም ሆነ አዲስ በሚፈጠረው ውህድ ፓርቲ ላይ የሚፈጥረው ተፅዕኖ እንደሌለ መረጋገጡ፣ አንድነት ከመኢአድ ጋር ውህደት በሚፈፅምበት ወቅት ሕጋዊ ሰውነቱን ወዲያውኑ ስለሚያጣ ከመድረክ ጋር የሚኖረው ግንኙነት ወዲያውኑ የሚቋረጥ በመሆኑ ችግር እንደማይፈጠር ተረጋግጧል ሲሉ ኢንጂነር ግዛቸው ተናግረዋል።

ሌላው ከጋዜጠኞች የቀረበው ጥያቄ፤ ቅድመ ውህደቱ የተሳካው በፓርቲዎቹ አመራሮች ሳይሆን፤ በሽማግሌዎች ግፊት ስለሆነ ምን ያህል ዘላቂነት ይኖረዋል የሚል ነበር። ለዚህ ጥያቄ ምላሽ የሰጡት ኢንጂነር ግዛቸው፤ በሁለቱ ፓርቲዎች መካከል የውህደት ፍላጎት መንፀባረቅ የጀመረው ከአራት ዓመት በፊት መሆኑን አስታውሰው፤ ለመዋሐድ ፍላጎቱ የመጣው ከአባሉና ከአመራሩ መሆኑን ጠቅሰዋል፤ ነገር ግን ሽማግሌዎቹ የመጡት በመጨረሻ ውህደቱ እንዲፋጠን ድጋፍ ለማድረግ ነው ብለዋል።

አቶ አበባው መሐሪ (የመኢአድ ሊቀመንበር) በበኩላቸው አንድነት ከመድረክ ጋር ስላለው ግንኙነት ሲመልሱ፤ እስካሁን ድረስ ውህደቱን ሲያጓትት የቆየው የአንድነትና የመድረክ ግንኙነት የጠራ ባለመሆኑ ነው ብለዋል። መኢአድ ከአንድነት ጋር ሲዋሐድ ይሄው ችግር ወደ ውህዱ ፓርቲ እንዳይሄድ በመፍራት ጥያቄው በመኢአድ በኩል መነሳቱን ገልፀዋል። ሆኖም ችግሩን የሚያጠና ሁለት ገለልተኛ የሕግ ባለሙያዎች ተመድበው የመድረክና የአንድነት እንዲሁም የመኢአድ ከምርጫ ቦርድ ሕግና ደንብ ጋር ታይቶ በመጨረሻ ወደ ውህዱ ፓርቲ ሊተላለፍ የሚችለው የገንዘብና የንብረት እንጂ የፖለቲካ ባለመሆኑ በዚሁ በመተማመን የቅድመ-ውህደት ሰነዱ ሊፈረም መብቃቱን ተናግረዋል።

ሽማግሌዎቹ በአደራዳሪነት ይሳተፉ እንደነበር የጠቀሱት አቶ አበባው፤ የሽማግሌዎቹ በጎ አስተዋፅኦ ቢኖርም፤ አሁን ግን ሁለቱ ፓርቲዎች ድርድሩን በራሳቸው የጨረሱት መሆኑን ገልፀዋል።

በተጨማሪነት ከጋዜጠኞቹ የቀረበው ጥያቄ ፓርቲዎቹ የውስጥ ችግራቸውን ሳይፈቱ ወደ ቅድመ-ውህደት ፊርማ ለምን መጡ? የቅድመ-ውህደት ፊርማው ከማካሄዱ በፊት በር ላይ ቅሬታ ሲያሰሙ የነበሩ ወገኖች ነበሩ ለሚለው ጥያቄ፤ አቶ አበባው ሲመልሱ በዚህ ወቅት ፓርቲዎቹ በውስጥ ችግር ላይ አለመሆናቸውን ይልቁኑ ቅድመ ውህደቱን እንዳይፈረም ሁከት የፈጠሩት የመኢአድ አባላት ሳይሆኑ የአዲስ አበባ የኢህአዴግ አባላት ናቸው ብለዋል። “የኢህአዴግ አባል የመኢአድን የውስጥ ችግር ይፈታ የማለት መብት የለውም” ሲሉ በመግለፅ ጉዳዩ ፓርቲዎቹን ውህደት እንዳይፈፅሙ በመንግስት በኩል የተቀናጀ ጥረት መኖሩን የሚያመለክት ከመሆኑም በላይ ኢህአዴግ ጠንካራ ፓርቲ እንዳይፈጠርና በሕዝባችን ላይ የጭቆና ቀንበር ጭኖ ለመቀጠል መፈለጉን የሚያመላክት ነው ብለዋል።

ፓርቲዎቹ ከሚያደርጉት ውህደት ጎን ለጎን በ2007ቱ ምርጫ የሚኖራቸው ተሳትፎና ለዚያም የሚሆን ስትራቴጂ ምን እንደሆነ ከጋዜጠኞች ተጠይቀው የነበረ ሲሆን፤ ምርጫውን በተመለከተ የውህዱ ፓርቲ የሚወስነው እንደሆነ ኢንጂነር ግዛቸው ጠቅሰው፤ በአጠቃላይ ሁለቱም ፓርቲዎች የምርጫ ፓርቲዎች እንደመሆናቸውና በሰላማዊ ትግል የሚያምኑ በመሆኑ ምንጊዜም ለምርጫ ዝግጁ መሆናቸውን አስረድተዋል። በአንድነት ፓርቲ በኩል አማራጭ ፖሊሲ የምርጫ ስትራቴጂ፣ ማኒፌስቶ፣ ማዘጋጀት ዕጩዎችንና ታዛቢዎችን እየፈተሸ መሆኑንና በመኢአድም በኩል ይሄው ጉዳይ ስለሚኖር የሁለቱንም አጣምረን እንቀጥላለን ብለዋል። በምርጫ መሳተፍ፣ አለመሳተፉ ግን ወደፊት እንደሚወሰንና የዴሞክራሲ ተቋማቱ ነፃ መሆንና መጠናከር ወሳኝ መሆኑን አብራርተዋል።

በጋዜጠኞች ከተነሱ ሌሎች ጥያቄዎች መካከል ከፓርቲዎች ውህደት በኋላ አንጃዎች የመፈጠር ሁኔታዎች ስለሚስተዋል ለዚህ ችግር የተቀመጠ ስትራቴጂ አላችሁ ወይ የሚል ነበር። ለዚህ ጥያቄ ምላሽ የሰጡት ኢንጂነር ግዛቸው፤ ውህደቱን ተከትሎ አንጃ መውጣቱ ፓርቲዎቹን እንደማያሳስባቸው ነገር ግን የሚወጣው አንጃ ስርዓት አልበኛ ሲሆን ነው ችግሩ ብለዋል። አንጃ የሚወጣ ከሆነም ሁለቱ ፓርቲዎች በተቀመጠው መዋቅር በዴሞክራሲያዊና በሰለጠነ መንገድ መወጣት ይቻላል። ነገር ግን በስርዓት አልበኝነት ቢሮ በመውረር ከኢህአዴግ ጋር በመገናኘት መሰናክል የመፍጠሩ አካሄድ አንጃ መፍጠር አይደለም ብለዋል።

“ውህደቱ አልተስማማኝም የሚል ቡድን ካለ መብቱ ነው። ሌላ ፓርቲ ማቋቋም ይችላል። የሰለጠነ ፖለቲካ ለማካሄድ የጉልበት፣ የመደባደብና ከባህል ውጪ የሆነ ነገር ሲሆን ግን ያሳፍራል” ሲሉ ኢንጂነሩ የገለፁ ሲሆን፤ በአሁኑ ወቅት ከዚህ አንፃር በአንድነት በኩል የሚያሰጋ ነገር የለም ብለዋል።

ውህደቱ በመዘግየቱ እንደተቋም ሁለቱን ፓርቲዎች በፍጥነት ባለመስራታቸው ኃላፊነቱን እንደሚወስዱ ሁለቱም አመራሮች ገልፀዋል። በተለይ አቶ አበባው መሐሪ ውህደቱ ለምን ዘገየ ለሚለው የጋዜጠኞቹ ጥያቄ ሲመልሱ፤ የፓርቲዎችን መዋቅርና የፖለቲካ ፕሮግራም በማጣጣም ሂደት እንጂ ከግል ፍላጎት አለመመቸት ጋር የተያያዘ አይደለም ብለዋል። በአጠቃላይ ከአንድ ወር በኋላ በሚጠራው ጠቅላላ ጉባኤ ከመኢአድ 200 ከአንድነት 200 የጠቅላላ ጉባኤ አባላት አዲስ ውህድ ፓርቲ ይፈጠራሉ ተብሎ ይጠበቃል።

የቅድመ-ውህደቱ ልዩ ገጠመኞች

የቅድመ-ውህደት ስነ-ስርዓቱን ልዩ ካደረጉት አጋጣሚዎች መካከል የኢትዮጵያውያን ዴሞክራሲ ፓርቲ (ኢዴፓ) አመራር አባል የሆኑት አቶ ሞሼ ሰሙ በፕሮግራሙ ላይ መገኘት አንዱ ነበር። የእሳቸው በቦታው መገኘት ከምርጫ 97 በኋላ ከፖለቲካ ልዩነት ባሻገር በግለሰብ ደረጃ የተፈጠረውን መቃቃር ሊያለዝብ የሚችል ጥሩ ጅምር እንደሆነም እየተገለፀ ነው። የአንድነትም ሆኑ የመኢአድ የፓርቲ አመራር አባላት ለአቶ ሞሼ ሰሙ ያሳዩት አዎንታዊ አቀባበል በዕለቱ የነበሩ ጋዜጠኞችን ትኩረት ስቦ ነበር። አብዛኛዎቹ የአንድነትና የመኢአድ አመራሮች አቶ ሞሼን ያገኙዋቸው ከምርጫ 97 በኋላ መሆኑን በአድናቆት ሲናገሩ ታይተዋል።

አቶ ሞሼ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ሰፊ የፖለቲካ ተሳትፎ እያሳዩ የመጡ ፖለቲከኛ ናቸው። በገዢው ፓርቲ ፖሊሲዎች ላይ ከሚያነሱዋቸው የሰሉ ትችቶች ባሻገር ለሀገሪቱ ፕሬስ መጠናከር የሚሰጡዋቸው ገዢ ኀሳቦች በመስኩ ባለሙያዎችና አጋሮቻቸው ጭምር እውቅና እየተሰጠው ነው። አቶ ሞሼ በሰኔ አንዱ የመኢአድና የአንድነት የቅድመ ውህደት ስምምነት ስነ-ስርዓት ላይ በድፍረት በመገኘታቸውም በኢዴፓ እና በሌሎች ተቃዋሚዎች መካከል ለረጅም ጊዜ የቆየውን ያለመተማመን ስሜት በመጠኑም ቢሆን እንዲለዝብ ምክንያት ሊሆን ይችላል ብሎ መገመት ይቻላል።

ሌላው በዕለቱ ስነ-ስርዓት ላይ ከታዩ አወዛጋቢ ጉዳዮች መካከል ሊጠቀስ የሚገባው የቅድመ ውህደት ስምምነቱን ለመረበሽ የተደረገው ጥረት ነው። የውህደቱን ስነ-ስርዓት ለማወክ የተደረገው ጥረት እንደ ሀገር የሚያሳፍር፣ እንደ ዜጋም የሚያሳዝን ነው።

ከአስተባባሪዎቹ ገለፃ መረዳት እንደሚቻለው የውህደት ስምምነቱ እንዳይካሄድ በር በመደብደብና ፀያፍ ቃል በመናገር ሲበጠብጡ የነበሩት ሦስት ግለሰቦች ነበሩ። በእርግጥ ስነ-ስርዓቱ ወደሚከናወንበት ስፍራ እንዲገቡ የተፈለገው አስቀድመው የተጠሩ እና ለዚያም ልዩ ባጅ ያደረጉ ብቻ ነበሩ። ሆኖም የተወሰኑ ሰዎች “ልግባ፣ አትገባም” የሚል ውዝግብ በሩ ላይ ይስተዋል ነበር። በመጨረሻም ውዝግቡ ተባብሶ በር እስከመገንጠልና ድንጋይ እስከመወራወር ተደረሰ። በመሀሉም በተወረወረ ድንጋይ በመኢአድና በአንድነት ከፍተኛ አመራሮች ላይ የጥርስ መውለቅ አደጋ በመድረሱ ሁኔታውን አሳዛኝ ትዕይንት አድርጎታል። በዕለቱም ስብሰባውን ከረበሹ ሦስት ሰዎች መካከል አንዱ የኢህአዴግ አባል መሆኑ ተገልጿል፡፡

በቅርቡ ሃያ ሦስተኛው የግንቦት ሃያ በዓል ሲከበር ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ ከተናገሩዋቸው በርካታ ርዕሰ ጉዳዮች መካከል ለሀገሪቱ መድበለ ፓርቲ መዳበርና ለተቃና የምርጫ ስርዓት ከተቀመጡ ሕጎችና አሰራሮች ባሻገር ኢህአዴግ አባላቱን በስነ-ምግባር በማነፅ ተከታታይ ስልጠና እየሰጠ መሆኑን፣ በሂደቱም የሚያጠፉ አባላቱን ለመቆጣጠር ከድርጅቱ የማንንም ምክር ሳይፈልግ በራሱ የእርምት እርምጃ እንደሚወሰድ መግለፃቸው አይዘነጋም።

ድምጻችን ይሰማ መግለጫ አወጣ፦ “በህዝበ ሙስሊሙ ወኪሎች ላይ በማረሚያ ቤት እየተደረገ ያለው ወከባ በአስቸኳይ ይቁም!”

$
0
0

ረቡዕ ሰኔ 4/2006

የታሰሩት ኮሚቴዎች

የታሰሩት ኮሚቴዎች

በሐሰት የሽብር ክስ ህገ መንግስታዊ መብቶችን በጣሰ ሁኔታ መሪዎቻችንን እያጉላላ የሚገኘው መንግስት በማረሚያ ቤት ውስጥ የሚያደርገውን ወከባ ቀጥሎበታል፡፡ ገና ወደማረሚያ ቤት ከተዛወሩበት ጊዜ አንስቶ ጠያቂዎችን በማጉላላት፣ የጥየቃ ሰአትን ከሌሎች በተለየ መልኩ በመገደብ፣ እንዲሁም በጠያቂዎች ቁጥር ላይ ገደብ በማድረግ በተለያዩ ወቅቶች መብታቸውን ሲነግፍ የቆየው መንግስት ዛሬ ደግሞ በታሪካዊው የካንጋሮ ፍርድ ቤት የችሎት ሂደት ምስክሮቻቸውን እያቀረቡና ትክክለኛው የህዝበ ሙስሊሙ ትግል ገጽታ በችሎት እየተመሰከረ ባለበት በዚህ ቅትት በፍርድ ቤት እየደረሰበት ያለውን ሽንፈት ለመቋቋም ወኪሎቻችን ላይ የተለያዩ ወከባዎችን እየፈጸመ ይገኛል፡፡ እስካሁን ድረስ በእስር ቤቱ ታሪክ በምንም መልኩ የማያስጠይቅን፣ ይልቁንም በማረሚያ ቤቱ ደንብ ጥበቃ የተደነገገለትን ገንዘብ የመያዝ መብት እንደወንጀል በመቁጠር በኮሚቴው ሰብሳቢ ኡስታዝ አቡበከር አህመድ እና በሸኽ መከተ ሙሄ ላይ፣ እንዲሁም በሌሎች ታሳሪዎች ላይ ሲያደርስ የነበረውና በቅርቡ የተረጋጋው ወከባ መሪዎቻችንን የማጥቂያ ሰበብ ፍለጋ እንጂ ሌላ እንዳልሆነ ግልጽ ነበር፡፡

አሁንም ይህንኑ ህገወጥ ድርጊቱን የቀጠለበት የእስር ቤቱ አስተዳደር በዞን አንድ በሚገኙ ጀግኖቻችን፣ (ማለትም በሸኽ መከተ ሙሄ፣ በኡስታዝ አቡበከር፣ በኡስታዝ ካሚል ሸምሱ፣ በኡስታዝ አህመድ ሙስጠፋ፣ በጋዜጠኛ አቡበከር ዓለሙ፣ በወንድም አብዱረዛቅ አክመል እና በወጣት ሙባረክ አደም) ላይ በዞን አንድ በሚገኙት 8 ክፍሎች እንዲበታተኑና እንዲለያዩ ትእዛዝ አስተላልፏል፡፡ ጓዞቻቸውንም ወደየተመደቡበት ክፍሎች እንዲቀይሩ እንደተነገራቸው ታውቋል፡፡ ባለበት የጤና ችግር ምክንያት ልዩ ትኩረትና ረዳት ጓደኛ የሚያስፈልገውን ወንድም አብዱረዛቅን ድጋፍ ለማግኘት አስቸጋሪ እንደሚሆንበት እያወቁ ብቻውን መድበውታል፡፡ ኡስታዝ አህመድ ሙስጠፋንም እንዲሁ ጊዜያዊ ማቆያ ተብሎ በሚታወቀውና በእስረኞች ቶሎ ቶሎ ተለዋዋጭነት ምክንያት ማህበራዊ ትስስር መመስረት አስቸጋሪ በሆነበት ክፍል ሆን ተብሎ እንዲመደብ ተደርጓል፡፡

የማረሚያ ቤቱ ደንብ በአንድ የክስ መዝገብ ችሎት የሚከታተሉ ታራሚዎች በችሎታቸው ዙሪያ በየጊዜው መነጋገርና መወያየት እንዲችሉ በአንድ ዞን የመታሰር መብት የሚሰጥ ቢሆንም አስተዳደሩ ግን ይህንን የሚያደርገው ሆን ብሎ የችሎታቸውን ፍሰት ለማስጓጎል እንደሆነ የአደባባይ ምስጢር ሆኗል፡፡ ሆነ ተብሎ እነሱን ብቻ የለየ ጥቃትና የመብት ጥሰት የሚፈጸምባቸውም በእስር ቤት ውስጥ ባለቻቸው ውስን ነጻነት የገነቧትን ማህበራዊ ትስስር ለማፍረስና የመጪውን ረመዳን ጾምም ተረጋግተው መጾም እንዳይችሉ ጫና ለማሳደር መሆኑ አያጠራጥርም፡፡ አወዛጋቢው የፍርድ ሂደት ቀጥሎ የሰው ምስክርነት እየተደመጠ ባለበት ሁኔታ የመጨረሻ ውሳኔ የማስለወጥ ሃይል ባይኖረውም እየተደመጠ ያለው ምስክርነት እጅግ እንዳደናገጣቸውና በዚህም ይህንን እርምጃ ለመውሰድ እንደተገደዱም የሚያሳብቅ ሆኗል፡፡ መንግስት በሃሰት የሽብር ክስ ማንገላታቱ ሳያንሰው በእስር ቤት ውስጥ እንኳን ታራሚዎች ላይ የሚያደርሰው በደል በእርግጥም የአገሪቱ የፍትህ ስርአት የቁልቁለት ጉዞውን እያፋጠነ ለመሆኑ ከበቂ በላይ ምስክር ነው፡፡

የእስር ቤቱ አስተዳደር ውስጥ ያሉት አንዳንድ ሀላፊዎች በግፍ እስር ላይ ለሚገኙት የህዝበ ሙስሊሙ ወኪሎች ያላቸውን ጥላቻ በተለያዩ አጋጣሚዎች ሲያሳዩ መቆየታቸው ይታወቃል፡፡ ካሁን ቀደም የደሴ ወጣት ታሳሪዎች ወደጨለማ ክፍል እንዲገቡ መወሰኑን ተከትሎ ሌሎች እስረኞች ተቃውሟቸውን ለማሰማት በተሰበሰቡበት ወቅት በቅጽል ስሙ ሻእቢያ ተብሎ የሚጠራው የማረሚያ ቤቱ የጸጥታ ሀላፊ ‹‹እኒህን አሸባሪዎች ይህን አጋጣሚ ተጠቅሞ መረሸን ነበር!›› ብሎ ቁጭቱን ሲገልጽ በግላጭ የተሰማ ሲሆን በተለያዩ አጋጣሚዎችም ጥቃት ከመፈጸም ወደኋላ እንደማይሉ መታዘብ ተችሏል፡፡ በማረሚያ ቤቱ ግቢ ውስጥ ካሁን ቀደምም በሌሎች በርካታ ታሳሪዎች ላይ አሰቃቂ የጅምላ ድብደባ ሲፈጸም የነበረ መሆኑ የቅርብ ጊዜ ትውስታ ነው፡፡

ህዝበ ሙስሊሙ ይህን መሰል የህገ መንግስቱን የእስረኛ አያያዝ ደንብ በግላጭ የሚጥሱ ወከባዎችና በደሎች በአስቸኳይ እንዲቆሙ ይጠይቃል! ህዝበ ሙስሊሙ ላይ ያወጁትን ጦርነት ሲያስፈጽሙ የቆዩት ደህንነቶችና የመዋቅራቸው አካላት ከህግ በላይ የሆነ አካሄዳቸውን በአስቸኳይ እንዲያቆሙም ያሳስባል! በህዝበ ሙስሊሙ ወኪሎች ላይ የሚፈጸም ማንኛውም ወንጀል በህዝበ ሙስሊሙ ላይ የሚፈጸም ወንጀል ነው፡፡ እነርሱ ላይ የሚደርስ በደል ፈርሞ ወደመንግስት በላካቸው ሰፊው ህዝበ ሙስሊም ላይ የሚደርስ በደል ነው፡፡ በመሆኑም በወኪሎቻችን ላይ አንዳች ነገር ቢደርስ ሃላፊነቱን ሙሉ በሙሉ የሚወስደው መንግስት መሆኑን እያስታወቅን ሰላማዊው ህዝበ ሙስሊምም ይህን መሰሉን ድንበር ያለፈ ጥቃት እስከመጨረሻው የሚፋረደው መሆኑን በጥብቅ እናሳውቃለን!

በህዝበ ሙስሊሙ ወኪሎች ላይ በማረሚያ ቤት ውስጥ እየተደረገ ያለው ወከባ በአስቸኳይ ይቁም!
የእስር ቤቱ አስተዳደር ከህግ በላይ መሆኑን በአስቸኳይ ያቁም!
የህዝብ ወኪሎችን ማጉላላት ይብቃ!
ድምፃችን ይሰማ!
አላሁ አክበር!


የሞረሽ እንቅስቃሴ ላልተገለጸለን አንዳንድ ነጥቦች

$
0
0

ከሞረሽ ደጋፊ፣ ረቡዕ ሰኔ ፫ ቀን ፪ሺህ፮ ዓ.ም.

moresh
ሞረሽ ወገኔ በወያኔ ዘረኛ የፖለቲካና ኢኮኖሚ ፖሊሲ፣ እቅድና እንቅስቃሴ መሠረት፣ በአገራችን በኢትዮጵያ በአማራ ጎሳ ላይ በየአቅጣጫው እየደረሰ ባለው መጠነ ሰፊ ጉዳት ምክንያት ብሶት የወለደው ድርጅት ነው። በሀገራችን ታሪክ ብዙ ሳንጓዝ «አምባገነን» የሚባለው የወታደራዊው ደርግ የግዛት ዘመን ሳይቀር፣ ጎሳዎችን ሳይለይ በፖለቲካ አመለካከት ምክንያት ኢትዮጵያውያንን በግድያ ንብረታቸውንም ለመንግሥት በማድረግና በመውረስ ከፍተኛ ጉዳት እንዳደረሰባቸው የቅርብ ጊዜ ትውስታ ነው። የአማራው ጎሳ አባላት እንደሌሎች ኢትዮጵያውያን ተጠቂ የነበሩ መሆናቸው የሚካድ አይደለም። በኢሕአፓም ሆነ በሌሎች የተቃውሞ ትግሎች የተሳተፉ፣ መስዋዕትነት የከፈሉ፣ በደርግ በኩልም በመሆን በተቃዋሚዎቹ ዒላማ ተደርገው የተገደሉ የዚሁ ጎሳ አባላት ብዙ ናቸው። ከዚያ በፊት የነበረውንም የቀዳማዊ አጼ ኃይለ ሥላሴ መንግሥት «ፍትሐዊ አይደለም» ብለው ከተነሱት የእንቅስቃሴ መሪዎችና ሰለባዎች ውስጥ ከአማራው ጎሳ የተወለዱ፣ ብዙ ለፍትሕ የቆሙ እንደነበሩ፣ ወያኔዎች ሳይቀር ይመሰክራሉ። ለአብነትም እነ የንዋይ ወንድማማቾች ብርጋዴር ጄኔራል መንግሥቱ እና ግርማሜ ንዋይ፣ ዋለልኝ መኮንን እና ሌሎችንም መጥቀስ ይቻላል። እነዚህ «የኢትዮጵያ አስተዳደር ትክክል አይደለም» በሚል መስዋዕትነትን የከፈሉ ከአማራ ጎሳ የተወለዱ ኢትዮጵያውያኖች እንጂ «አማራ ነን» በሚል የተንቀሳቀሱ አልነበሩም።


ወያኔዎች በኢትዮጵያ ውስጥ በቁጥር አናሳ መሆናቸውን ስለሚገነዘቡ፣ በስልጣን ይቀናቀነኛል የሚሉትን ወገን ሌሎችን አስተባብሮ ማጥቃት እንደ ስትራተጂ የሚጠቀሙበት ነው። በመሆኑም በኢትዮጵያ ተፈጥረው ለነበሩ ችግሮች ብቻ ሳይሆን ያልነበረ ችግርን እንደነበረ አድርጎ፣ ለዚህም የአማራውን ጎሳ ተጠያቂ ማድረግ፣ የአጭር ጊዜ ፍላጎቱን እንደሚያሳካለት በማሰብ ነው። ስለሆነም በትላልቅ ጎሳዎችም ሆነ በአናሳ ጎሳዎች እንዲጠላና ዘመቻ እንዲካሄድበት፣ ከፍተኛ የሆነ የጥፋት ሥራ ሠርቷል። የዋህ የሆኑ የዚህ የወያኔ እኩይ የሆነ አስተሳሰብ ሰለባ የሆኑ ጎሳ አባላትም ለዘመናት አብረዋቸው የኖሩ የአማራ ጎሳ ተወላጂ የሆኑ ጎረቤቶቻቸው ላይ ከ«ውጡልን» አንስቶ እስከ ግድያ የሚደርሱ ብዙ በደሎች ሲደርስባቸው በጥቃቱ በመተባበር ወይም ዝም በማለት አሳልፈዋል፣ ወይም በማሳለፍም ላይ ናቸው። ይህንን በአማራው ጎሳ ላይ ያነጣጠረ ጭፍን ጥላቻ ማንኛውም ፍትሕን የሚሻ ዜጋ ሁሉ ሊቃወመውና ሊያስቆመው ይገባ ነበር። ሆኖም ግን ወያኔ አገሪቱን ከተቆጣጠረ ጀምሮ በአማራው ጎሳ ላይ የሚያደርሰውን ጥቃት በተጠናከረ መልኩ ሲፈጸም እናያለን።


በተደራጀ ኃይል ጥቃት የሚደርስባቸው ተጠቂዎች ከሚደርስባቸው ጥቃት ሲሸሹና የመጠቃት ፍራቻ ሲኖራቸው በጋራ መከላከልን መሻት ተፈጥሯዊ ክስተት ነው። በኢትዮጵያ ውስጥ ዘርን መሠረት ያደረገ የፖለቲካ አደረጃጀት መኖር እንደሌለበት የሞረሽ ወገኔ መሥራቾች ጠንቅቀው ያውቃሉ። የፖለቲካ ድርጅቶች ዘርን መሠረት ሲያደርጉ የእድገት ደረጃን ያለማወቅና ሰዎችን አንድ የሚያደርጋቸው ቀለማቸው፣ ቋንቋቸው ወይም ባህላቸው ብቻ ሳይሆን አመለካከታቸው መሆኑን አለመገንዘባቸውን የሚያሳይ ነው። የሞረሽ መሥራቾች የወያኔን የጎሳ ፖለቲካ ቢቀበሉት ኖሮ ቀደም ብለው የፖለቲካ ድርጅት በመሠረቱ ነበር። ከሁለት አሥርት ዓመታት በላይ መጠበቅም ባላስፈለገ ነበር።


ሞረሽ እንደ መርህ በየትም ቦታ የተረገጠች ፍትሕን ትክክል አይደለም ብሎ ያምናል፣ እንዲስተካከልም ድምጽ ያሰማል። በመሆኑም በኦሮሞም፣ በጋምቤላም፣ በሶማሌም፣ በትግሬም ወይም በሌሎች ጎሳዎች በገዢውም ሆነ በሌላ ሥልጣን ፈላጊ ቡድን የሚደርሰውን ጥቃት ሁሉ አጥብቆ ይቃወማል። ሞረሽ ኢትዮጵያ የብዙ ጎሳዎች ደሴት እንደመሆኗ መጠን አንዱ ጎሳ ተጎድቶ ወይም አንዱ ጎሳ የሌለበት ኢትዮጵያ አትኖርም ብሎ ያምናል። ስለሆነም የአማራ ጎሳ የሌለባት ኢትዮጵያ ኢትዮጵያ አትባልም፣ የኦሮሞ ጎሳ የሌለባት ኢትዮጵያ ኢትዮጵያ አትባልም፣ የትግሬ ጎሳ የሌለባት ኢትዮጵያ ኢትዮጵያ አትባልም እንዲሁም ሌሎች ጎሳዎች የሌሉባት ኢትዮጵያ

ኢትዮጵያ አትባልም። በመሆኑም አንዱ ሲበደል ተበዳዩ ብቻ ሳይሆን ሌላውም ሁሉ ቁጭቱን ሊገልጽና ድርጊቱን ሊቃወመው ይገባል። ያ ሲሆን የሚፈራው ሥልጣን የያዘው ሳይሆን ሕዝብ ይሆናል ማለት ነው። ትክክለኛው ፍርሀትም ይሄው ነው።


ሞረሽ በዚህ መርሁ የማንኛውም ጎሳ አባላት በግልም ይሁን በቡድን መበደል የተቃውሞ ድምጹን አጉልቶ ያሰማል። ሌሎች ጎሳዎች በዛ ያሉ ድምጽ የሚያሰሙ ቡድኖችና ድርጅቶች ቢኖሯቸውም የአማራው ጎሳ ግን በታላቁ የኢትዮጵያ ልጅ በፕሮፌሰር አሥራት ተጀምሮ ከነበረው መአሕድ በስተቀር ለጎሳው አቤቱታ የሚያሰማ፣ እየደረሰበት ያለውን ጉዳት የሚቃወም፣ የተሰባሰበ ቡድን የለውም። በሌላ በኩል ግን በወያኔ መንግሥት አስተባባሪነት በአማራው ጎሳ ላይ በየቦታው እየደረሰ ያለው ጉዳትና ጥቃት ለመለካት የሚያስቸግር ነው። በመሆኑም ሞረሽ ወገኔ በአማራው ጎሳ ላይ የሚደርሰውን ጉዳት ለማሳወቅ አቅሙ የፈቀደውን ትግል የሚያደርግ ከመሆኑም በተጨማሪ ሌሎች አግባብነት ያላቸው መንገዶችን በመጠቀም በደል የሚፈጽሙትና የሚያስፈጽሙትን ከሕግ ፊት ለማቅረብ የበኩሉን ጥረት ያደርጋል። ሞረሽ ወገኔ ለአማራው የሚመኘውን ሰብአዊ፣ ዲሞክራሲያዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ሌሎች መብቶች ለማንኛው የሀገሪቱ ጎሳ አባላት እንደሚመኚና ለተፈጻሚነቱም ድምጹን በማሰማት የመታገያ ስልቱ አስፈላጊውን ሁሉ ያደርጋል። በዚህ አጋጣሚ ሞረሽ ሊገልጸው የሚፈልገው ነገር ቢኖር አሁን ባለበት ሁኔታ የሲቪክ ድርጅት እንጂ የፖለቲካ ድርጅት አለመሆኑን ነው። እንደ ሞረሽ እምነት የጥቁሮችን መብት በማስከበር በእንቅስቃሴ ውስጥ ነጮች እንደተሳተፉና መስዋዕትነት እንደከፈሉ ሁሉ የአማራው ጎሳ የሚደርስበትን በደል «አግባብ አይደለም» ለማለትና የሚደርስበትን በደል ለማስቆም የየትኛውም ጎሳ አባላት ተሳትፎ ማድረግ አግባብነት አለው ይላል።


የሀገራችን ታሪክ እንደማንኛውም ሀገር ታሪክ መልካምም መጥፎም ገጽታ ይኖረዋል። የሰው ልጅ የሠራው ሥራ የሚገመገመውም በወቅቱ ባለው መለኪያ እንጂ ዘመናትን አሻግሮ በማይመሳሰሉ ዘመናት ባሉ መለኪያዎች መሆን የለበትም። ያለፈውን መልካም ነገር መሠረት አድርጎ ከተሠሩ ስህተቶች ተምሮ መልካም ነገርን ማምጣትና በእጁ ያለውን የአሁኑን ጊዜ በሚገባ በመጠቀም ወደፊት የሚፈጠር እውነታን መቀየርና የሚጻፍ ታሪክን መልካም እንዲሆን ማድረግ ተገቢ ነው። ይህ ለጋራ ዕድገት የተሻለ ነገርን ያመጣል። ያለፈ አፈ ታሪክ ላይ በማተኮር እድገት አይመጣም። እድገት የሚመጣው በአግባቡ የተተለመ ራዕይ ላይ በማተኮርና ተገቢውን በመተግበር ነው። በጥላቻ እድገት አይመጣም። ጥላቻ የሚያመጣውን ውጤት ለማየት ብዙ መመራመር አያስፈልግም። በዓለም ላይ ያሉ ትላልቅ ችግሮች የጥላቻ ውጤቶች ናቸው። ሞረሽ ይህንን ጠንቅቆ ያውቃል። በአማራው ላይ በወያኔ መሪነት በመጀመሪያ በሌሎች ጎሳዎች ጥላቻ እንዲደርስበት ከዚያም በመቀጠል በንብረቱና በሕይወቱ ላይ ጉዳት እንዲደርስበት ሲደረግ ከሁለት አሥርት ዓመታት በላይ ተቆጥሯል። ልብ እንበል፥ በእናት ማህጸን ውስጥ ያሉ ያልተወለዱ ጽንሶች፣ ምንም የማያውቁ ሕጻናት ሳይቀር ታርደው እንዲገደሉ ተደርጓል። ሠርተው ከመብላት ውጭ ምንም የፖለቲካ አስተሳሰብና የሥልጣን ፍላጎት የሌላቸው ገበሬዎች ከኖሩበትና ሀብትና ንብረት ከአፈሩበት ቦታ ያለምንም ነገር ባዶ እጃቸውን ተፈናቅለው ቤት አልባ መንገድ ተዳዳሪ ለማኞች እንዲሆኑ ተደርገዋል። ይህንን ድርጊት በተደራጀ መልኩ መቃወምና ማስቆም የግድ ይሆናል። ለዚህም ነው ሞረሽ ወገኔ የአማራ ድርጅት የተቋቋመው። በመሆኑም ሞረሽ በወያኔ የፖለቲካ ፍልስፍና መሠረት የተፈጠረ ሳይሆን በወያኔ እኩይ ሥራ ምክንያት መጠነ ሰፊ የሆነ የጥፋት ዘመቻ እየደረሰበት ያለውን የአማራ ጎሳ ለመታደግ የበኩሉን አስተዋጽኦ ለማድረግ የተቋቋመ ነው።

የዘንድሮው የዓለም ዋንጫ እውነታዎች –ይህን ሳያነቡ ጨዋታው እንዳይጀመር!

$
0
0

Fifa-World-Cup-2014-Brazil(ሰንደቅ ጋዜጣ)

በየአራት አመቱ የሚካሄደው ተወዳጁ የእግር ኳስ ስፖርት መድረክ፣ የአለም ዋንጫ የአለም ደረስኩ ደረስኩ እያለ ነው። ብራዚል ለሁለተኛ ጊዜ የምታስተናግደው 20ኛው የአለም ዋንጫ ሊጀመር አንድ ሳምንት ይቀረዋል። የስፖርቱ አፍቃሪ የአለም ህዝብ ሁሉ የውድድሩን መጀመር በታላቅ ጉጉት እየጠበቀ ነው። ተሳታፊ ሀገሮችም ወደ ደቡብ አሜሪካዊቷ ሀገር እያቀኑ ነው። 


በስምንት ምድብ የተደለደሉ 32 ብሔራዊ ቡድኖች ለአንድ ወር የሚያደርጉትን ፉክክር በብራዚል12 ከተሞች ይስተናገዳሉ። አስተናጋጇ ብራዚል ከክሮሺያ የምታደርገውን የመክፈቻ ጨዋታ በሳኦ ፖሎ አሬና ደ ሳኦፖሎ ወይም አሬና ኮሮንቲያስ ተብሎ በሚጠራው ስታዲየም ይካሄዳል። የፍጻሜው ጨዋታ ደግሞ በ1950 የአለም ዋንጫ ብራዚል በፍጻሜ ጨዋታ በኡራጓይ ተሸንፋ ዋንጫ ባጣችበት በሪዮ ዴ ጄኔሪዮ ከተማ በሚገኘው ግዙፉ ማራካኛ ስታዲየም ይስተናገዳል።
የ2014 የፊፋ የአለም ዋንጫ ለአንድ ወር ያህል ጊዜ ሲካሄድ አስገራሚ ክስተቶችም እንደሚታይበት ይጠበቃል። የአለም ዋንጫውን ከወዲሁ ልዩ የሚያደርጉት በርካታ እውነታዎችም እንዳሉ ይታወቃል። ከነዚህም መካከል የተወሰኑት በዚህ ጽሁፍ ተካተዋል።

በተቃውሞ ድምጾች የሚታጀብ የአለም ዋንጫ
በአለም ዋንጫ ሲቃረብ ታዲያ የአለም መገናኛ ብዙሀንን የሳበው እንደወትሮው በውድድሩ ሻምፒዮና የሚሆኑ ቡድኖችና ኮከብ ተጫዋቾች ጉዳይ አይደለም። ከሁሉም በላይ መነጋገሪያ የሆነው ውድድሩን የሚካሄድባቸው ስታዲየሞች በተያዘላቸው የጊዜ ገደብ መሰረት አለመጠናቀቃቸውና የአለም ዋንጫውን ከፍተኛ ወጪን የተቃወሙ ብራዚላውያን ጉዳይ ነው። የተቃውሞ ሰልፉ እየተጠናከረና እየተስፋፋ መምጣቱ የአለም ዋንጫውን ስኬታማነት ላይ ስጋት አሳድሯል።
የውድድሩ አዘጋጆች ግን ውድድሩ በታቀደው መሰረት በስኬት ይጠናቀቃል እያሉ ነው። የብራዚል መንግስትም ሆነ ፊፋ የአለም ዋንጫው ምንም እክል እንዳይገጥመው እናደርጋለን ቢሉም የሚሳካላቸው አይመስልም።
ሰሞኑን ከኳታር የ2022 የአለም ዋንጫ አዘጋጅነት ጋር በሙስና እየተብጠለጠለ የሚገኘው ፊፋ ለብራዚል ያለውን ጠንካራ ድጋፍ በተደጋጋሚ ገልጿል። ከሶስት አመት በፊት ጡረታ እንደሚወጡ ተናግረው የነበሩትና አሁን ደግሞ በቀጣዩ ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ እሳተፋለው ያሉት ሴፕ ብላተር ‹‹ሀገሪቱ ዝግጅቷ የተጓተተ ቢሆንም የአለም ዋንጫውን እንድታስተናግድ መመረጧ ግን ተገቢ ነው›› ብለዋል።
ይሁንንና የድግሱ ባለቤቶች ብራዚላውያን ከ50 አመት በኋላ ወደ ቤታቸው የመጣውን የአለም ዋንጫ በተወዳጁ የሳምባ ዳንሳቸው አድምቀው በክብር የሚቀበሉት አልሆኑም። ‹የኑሮ ውድነት ጣሪያ ነክቷል፣ የአለም ዋንጫ አሁን ላይ ዳቦ አይሆነንም› ያሉ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ዜጎች አደባባይ ወጥተው ቅሬታቸውን እያሰሙ ነው። ‹‹ትበላው የላት ትከናነበው አማራት›› የሚለውን የኢትዮጵያውያን አባባል የሚያስታውሱ ብራዚላውያን ምሬቶች ጎልተው እየተሰሙ ነው። ብራዚላውያኑ ‹ትምህርት ቤቶችና የጤና ተቋማት፣ በቂ የመጓጓዣ አውቶብሶችና ባቡሮች ሳይኖሩን መንግስት ለአለም ዋንጫ ብሎ ስታዲየም በማሰራትና በማደስ ከፍተኛ ገንዘብ አውጥቷል› ሲሉ ወቀሳቸውን ያሰማሉ። የአለም ዋንጫ መዘጋጀቱ ብቻ ሳይሆን ከሀገሪቱ ደሀ ዜጎች ላይ በግብር የሚሰበሰብ መሆኑ ነው ይበልጥ ያስቆጣቸው።
ብራዚላውያን ምንም እንኳን የእግር ኳስ ፍቅር በደማቸው ውስጥ የሰረጸ ቢሆንም የአለም ዋንጫ ለድህነት የሚዳርጋቸው ከሆነ አዘጋጅነቱ ወደ ምድራቸው ባይመጣ ይመርጣሉ። ከአመት በላይ የዘለቀው ተቃውሟቸውም የአለም ዋንጫው ሲጀመር እንደሚጋጋል ይጠበቃል። በይበልጥ ደግሞ ቡድናቸው ለፍጻሜ የማይደርስና በጊዜ የሚሰናበት ከሆነ የከፋ ትርምስ መፈጠሩ አይቀርም። ቡድናቸው ዋንጫ ቢወስድም እንኳ ተቃውሟቸውን ከመግለጽ እንደማያግዳቸው መገመት ይቻላል። ለዚህም ደግሞ በ2013 የኮንፌዴሽን ዋንጫ ቡድናቸው አሸንፎ እንኳ በመንግስት ላይ ቅሬታቸውን ከመግለጽ ያልተቆጠቡበትን አጋጣሚ ማስታወስ ተገቢ ነው።

የጎል መስመር ቴክኖሎጂ
ባለፉት ጊዜያት በአለም ዋንጫ መድረኮች ላይ በርካታና አይረሴ አወዛጋቢ የጎል ውሳኔዎች ታይተዋል። በብራዚሉ የአለም ዋንጫ ግን መሰል ድርጊት አይኖርም። የጎል መስመር ቴክኖሎጂ ለመጀመሪያ ጊዜ ተግባራዊ የሚሆንበት የመጀመሪያው የአለም ዋንጫ ይሆናል። በአለም ዋንጫው ወቅት አርቢትሮች በስታዲየሙ ዙሪያ በተገጠሙ 14 ካሜራዎችና ኮምፒውተር ቴክኖሎጂ እየታገዙ ጎል መቆጠሩን ያረጋግጣሉ። ይኸውም ለግብነት የተሞከረች ኳስ የግብ መስመሩን የምታልፍ ከሆነ አርቢትሮች እጃቸው ላይ በሚያስሩት ልዩ ሰአት አማካኝነት ንዝረት ይሰማቸዋል። ‹ጎል› የሚል የዕሁፍ መልዕክትም ይታያቸዋል።
ሌላው በብራዚሉ የአለም ዋንጫ ተግባራዊ የሚሆነው ቴክኖሎጂ በስታዲየም ውስጥ ደህንነትንና ጸጥታን ከማስጠበቅ ጋር በተያያዘ የሚሰማሩ ሮቦቶች መኖራቸው ነው። ሮቦቶቹ የደህንነት ስጋት የሚሆኑ ክስተቶችን አስቀድመው የሚጠቁሙ ማንቂያ ምልክቶችና ድምጾችን የሚያመለክቱ ናቸው። ከዚህ በተጨማሪም በስታዲየሙ ውስጥ አላስፈላጊ የሆኑ እንቅስቃሴዎችንና ረብሻዎችን መቆጣጠር የሚችሉ ሮቦቶች ይሰማራሉ። እነዚህ ሮቦቶች በስታዲየም ፖሊሶችን ስራ እንደሚያቀሉ ታምኖባቸዋል።

ውዱ የአለም ዋንጫ መድረክ
የብራዚሉን የ2014 የአለም ዋንጫ ለየት ከሚያደርጉት እውነታዎች መካከል ዋንኛው እስከ አሁን ከተካሄዱ የአለም ዋንጫዎች ሁሉ ከፍተኛ ወጪን በመጠየቅ ቀዳሚው መሆኑ ነው። ብራዚል ለአለም ዋንጫው ከ14 እስከ 16 ቢሊዮን ዶላር እንደሚፈጅባት ተነግሯል። ይኽም ወጪ ባለፉት ሶስት የአለም ዋንጫዎች አጠቃላይ ወጪ እጥፍ መሆኑ ነው። ከሁሉም በላይ ደግሞ ከፍተኛ ወጪ የተባለው ለስታዲየም ግንባታና እድሳት ከ1ቢለዮን ዶላር በላይ ያወጣችው ወጪ ነው። ገንዘቡ ደግሞ ከደሀው ህዝብ ከግብር የሚሰበሰብ መሆኑ ህዝቦቿን ለአደባባይ ተቃውሞ አብቅቷቸዋል።
የአለም ዋንጫው በዝግጅት ብቻ ሳይሆን በተለያዩ አገልግሎቶች በኩልም ከፍተኛ ወጪን የሚጠይቅ መሆኑ ተጠቅሷል። በውድድሩ ወቅት የሆቴሎች፣ የምግብና መጠጥ እንዲሁም ሌሎች አገልግሎቶች ዋጋቸው የትየሌለ ነው ተብሏል። የአለም ዋንጫውን ተከትሎ በብራዚል በሁሉም መስክ የሚሰጡ አገልግሎቶች ዋጋ በከፍተኛ መጠን ንሯል። በተለይም ውድድሩን ለመመልከት ከተለያዩ የአለም ክፍሎች ወደ ብራዚል የሚጓዙ ከ600ሺ በላይ የውጭ ሀገር ዜጎች ከፍተኛ የሆነ የዋጋ ጭማሪ ይጠብቃቸዋል።

የመክፈቻ ንግግር የሌለው የአለም ዋንጫ
የአለም ዋንጫ ውድድር ሁልግዜም በመክፈቻ ዝግጅቶች ይደምቃል። በክብር እንግዶች የመክፈቻ ንግግር አማካኝነትም ውድድሩ በይፋ መጀመሩ ይበሰራል። የብራዚሉ የ2014 የአለም ዋንጫ ግን ያለ መክፈቻ ንግግር ነው የሚጀመር መሆኑ ልዩ ያደርገዋል። ምክንያቱ ደግሞ የመክፈቻ ንግግር ሲደረግ የአለም ዋንጫውን የሚቃወሙ የብራዚላውያን ድምጾች እንዳይሰሙ ለማድረግ ነው።
ባለፈው አመት ብራዚል የኮንፌዴሬሽን ዋንጫን ስታዘጋጅ የሀገሪቱ ፕሬዝዳንት ዳይላማ ሩሴልፍና የፊፋው ፕሬዝዳን ሴፕ ብላተር የመክፈቻ ንግግር ሲያሰሙ ንግግራቸው በስታዲየሙ በነበሩ ብራዚላውያን የተቃውሞ ድምጽ ሊሰማ አልቻለም ነበር። በአለም ዋንጫው የመክፈቻ እለትም ብራዚላውያን መሰል የተቃውሞ ድምጽ እንደሚያሰሙ በመገመት ምንም አይነት የመክፈቻ ንግግር እንዳይደረግ ተወስኗል።

የቡድኖች ልዩ ፍላጎቶች
በአለም ዋንጫ የሚሳተፉ ብሔራዊ ቡድኖች ምቾታቸው እንዲጠበቅና ምንም ቅሬታ እንዳይሰማቸው አስተናጋጇ ሀገር የምትችለውን ሁሉ ጥረት ታደርጋለች። ለዚህም ተሳታፊ ቡድኖች በሚያርፉበት ሆቴል ውስጥ እንዲኖር የሚፈልጓቸው ነገሮችንና ሁኔታዎች እንዲያሳውቋት አስቀድማ ትጠይቃለች።
በብራዚሉ የአለም ዋንጫም ቡድኖች በሆቴላቸው ውስጥ እንዲሟሉላቸው የሚፈልጓቸው ነገሮች ተጠይቀው ምላሻቸውን አሳውቀዋል። አንዳንዶቹ ተገቢና ስሜት የሚሰጡ ሲሆን፣ አግራሞትን የሚፈጥሩም ይኖራሉ። አርት52 የተሰኘ የእንግሊዝ ድረገጽ አስገራሚ ካላቸው የብሔራዊ ቡድኖች ፍላጎቶች ያላቸውን ጠቅሷል። በቀዳሚነትም የኡራጓይ ቡድን ልዩ ፍላጎትን ጽፏል። ሞቃታማው የብራዚል የአየር ንብረት ያሳሰበው የኡራጓይ ብሔራዊ ቡድን በሆቴሉ ውስጥ ምንም ድምጽ የሌለው አየር ማቀዝቀዛ እንዲኖር ጠይቋል።
የፖርቹጋል ብሔራዊ ቡድን ደግሞ በሆቴሉ ውስጥ ኮምፒውተሮች እንዲሟሉለት የጠየቀ ሲሆን፣ ጃፓኖች ጃኩዚ በእያንዳንዱ መኝታ ክፍል ውስጥ እንዳይቀርብን ብለዋል። አልጄሪያዎች ቅዱስ ቁርአን በሆቴላቸው ውስጥ ማግኘት እንደሚፈልጉ አሳውቀዋል።
የማንቸስተር ሲቲውን ቅንጡ አማካኝ ተጫዋች ሳሚር ናስሪን ያላካተተው የፈረንሳይ ብሔራዊ ቡድን ደግሞ በበሆቴል ውስጥ ለአባላቱ ደረቅ ሳሙና ሳይሆን ፈሳሽ ሳሙና ብቻ እንሚፈልግ አስታውቋል። ኢኳዶራውያን ደግሞ በእያንዳንዱ ክፍላቸው ውስጥ ሁሌም ሙዝ ማጣት እንደማይፈልጉ ነው የገለጹት።

የኢትዮጵያ ነፃ ጋዜጠኞችንና ጦማርያንን ማን ይፈራቸዋል?

$
0
0
ከፕሮፌሰር አለማየሁ ገብረማርያም ትርጉም በነጻነት ለሀገሬ እስክንድር ነጋን፣
 ርዕዮት ዓለሙን፣ ውብሸት ታዬን፣ የዞን ዘጠኝ ጦማሪዎችንማን ይፈራቸዋል?
bloggersየኢትዮጵያ የነጻው ፕሬስ እና ጦማርያን ቁንጮ የሆነው እስክንድር ነጋ ሀሳቡን በነጻ በመግለጹ ብቻ በአምባገነኑ የወሮበላ ቡድን ስብስብ የይስሙላው የዝንጀሮ ፍርድ ቤት የ18 ዓመታት እስር ተበይኖበት በገዥው አካል የማጎሪያ እስር ቤት በመማቀቅ ላይ ይገኛል፡፡ ሟቹ መለስ ዜናዊ ልዩ ትዕዛዝ እስክንድር ነጋ በቁጥጥር ስር እንዲውል እና የ18 ዓመቱ የሸፍጥ እስራት እንዲበየንበት ተደርጓል፡፡ መለስ ዜናዊ በኢትዮጵያ ከሚገኙ ማናቸውም ጋዜጠኞች የበለጠ እስክንድር ነጋን ይፈራዉና ይጠላው ነበር፡፡ ዝሆን አይጦችን “ይፈራል” ከሚለው ኢ-ስነ አመክንዮ አንጻር በተመሳሳለ መልኩ መለስም እስክንድር ነጋን እንደጦር ይፈራው ነበር፡፡
በቅርቡ እስክንድር ከማጎሪያው እስር ቤት ለ8 ዓመት ልጁ ለናፍቆት እንዲህ የሚል ግልጽ ደብዳቤ ጽፏል፣ “እንዲያው ሁኔታውን ሳየው እያለሁ የሌለሁ የዘፈቀደ አባት ሆኛለሁ፣ ምክንያቱም በ18ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ፈረንሳዮች ነጻነት፣ እኩልነት፣ ፍቅር እያሉ ደጋግመው ይጠሯቸው የነበሩትን ሶስት ቀላል ቃላትን በመውሰድ እኔም በሀገሬ ነጻነት፣ እኩልነት እና ፍቅር እንዲሰፍን በማሰብ እነዚህን ቃላት በማስተጋባቴ ነው በሸፍጠኞች ለእስር የተዳረግሁት“ ብሏል፡፡ እስክንድር ለነጻነት፣ ለእኩልነት እና ለአብሮነት ፍቅር ጦማሪ ነው፡፡ ለዚህም ነው ለእኔ የጀግናዬ ተምሳሌት የሚሆነው!
የኢትዮጵያ የፕሬስ ነጻነት ቀንዲል ጀግናዋ የ34 ዓመቷ ወጣት ርዕዮት ዓለሙ በተመሳሳይ መልኩ በአቶ መለስ ዜናዊ የ14 ዓመታት እስር በይኖባታል፡፡ ይህች ጀግና ወጣት በዓለም አቀፉ ህብረተሰብ ዘንድ “እውነት ተናጋሪዋ ኢትዮጵያዊት እስረኛ” በመባል ትታወቃለች፡፡ ርዕዮት ለእስር የተዳረገችው የግድብ ፕሮጀክት የገንዘብ ማሰባሰቢያ ዘዴዎችን በተመለከተ በገዥው የፖለቲካ ፓርቲ ላይ ጠንካራ ትችት በማቅረቧ እና በቅርቡ በህይወት የተለዩት የሊቢያ አምባገነን መሪ ሙአማር ጋዳፊ እና መለስ ዜናዊ ከአንድ ባህር የሚቀዳ ተመሳሳይ ባህሪ ያላቸው መሆናቸውን በይፋ በመግለጿ ነው፡፡ ርዕዮት በእስር ቤት ተዘግቶባት እና አፏን ተሸብባ ለመቀመጥ ባለመፍቀድ በድፍረት አንገቷን ቀና አድርጋ ስልጣኖቻቸውን ከህግ አግባብ ውጭ በህገወጥነት ለሚጠቀሙት ህገወጦች እና ትዕቢተኞች እውነት እውነቱን እንዲህ በማለት እቅጬን ተናግራለች፣ ”የተሻለች ኢትዮጵያን ለማየት እኔ በግሌ የሚጠበቅብኝን ሁሉ ማበርከት አለብኝ የሚል እምነት አለኝ፣ በአሁኑ ጊዜ በኢትዮጵያ ውስጥ በርካታ ኢፍትሀዊነቶች እና ጭቆናዎች ተንሰራፍተው ስለሚገኙ እነዚህን እኩይ ተግባራት በምጽፋቸው ትችቶቸ ማጋለጥ እና ከንቱ መሆናቸውን መቃወም አለብኝ… ለዚህ በጎ ዓላማ በድፍረት ትግል በማካሂድበት ወቅት ሊያስከፍለኝ የሚችለውን ዋጋ ሁሉ ለመቀበል ዝግጁ ነኝ“ በማለት ከእስር ቤት አፈትልከው በሚወጡ የእጅ ጽሁፎቿ ገልጻለች ጀግናዋ ርዕዮት ዓለሙ፡፡ በማይበገረው እና በማይንበረከከው ትክክለኛ የጽናት አቋሟ ምክንያት ገዥው አካል ሰብአዊነት የሚባለውን ክቡር ነገር በመደፍጠጥ የህክምና አገልግሎት እንዳታገኝ ቅጣት ጥሎባታል፡፡ መቀመጫውን ሎንዶን ያደረገ የህግ መከላከል የተነሳሽነት ሜዲያ/Media Legal Defense Initiative የተባለ ተቋም በአልጃዚራ ባቀረበው ዘገባ መሰረት ርዕዮት “በሰውነት አካሏ ላይ የተከሰተ እብጠት የተገኘ ቢሆንም ተገቢ የሆነ ህክምና እየተሰጣት እንዳልሆነ ግልጽ አድርጓል፡፡ ምንም ዓይነት የሰመመን መስጫ ማደንዘዣ ሳይሰጣት በጡቷ ላይ የቀዶ ህክምና ስራ በማከናወን የቀዶ ህክምና መስፊያ ክሩ ከጡቷ ሳይወጣ ከዓመት በላይ ከመቆየቱም በላይ ከደህረ ቀዶ ህክምናው በኋላም ቢሆን ተገቢ የሆነ ህክምና የተሰጣት አይደለም“ ብሏል፡፡ ለእኔ ርዕዮት የጀግና ተምሳሌታዬ ናት!
የማይበገረው ጋዜጠኛ እና አርታኢ ውብሸት ታዬ የመናገር አንደበቱን ተሸብቦ በመለስ ዜናዊ ዝዋይ በሚባል አስፈሪ እና ጭራቃዊ የማጎሪያ እስር ቤት በመማቀቅ ላይ ይገኛል፡፡ በእርሱ ላይም የ14 ዓመታት እስራት ተበይኖበታል፡፡ ውብሸት የገዥውን አካል ሙስና እና ስልጣንን ከህግ አግባብ ውጭ መጠቀምን አስመልክቶ በጋዜጣ ላይ የሚያቀርባቸውን ትችቶች እና አስተያየቶች በፍጹም አያቋርጥም፡፡ ውብሸት ለሚጠዘጥዝ የኩላሊት ህመም ተጋልጦ የሚገኝ ቢሆንም እርሱም ህክምና እንዳያገኝ ተደርጎ በመሰቃየት ላይ ይገኛል፡፡ በኢትዮጵያ በማጎሪያው እስር ቤት ለሚገኙት የህሊና እስረኞች የህክምና አገልግሎት መንፈግ በኢትዮጵያ ያለው ገዥ አካል እለት በእለት የሚፈጽማቸው በሰው ልጆች ላይ የሚፈጸሙ የቅጣት ወንጀሎች ናቸው፡፡ ፍትህ እየተባለ የሚጠራው የውብሸት የአምስት ዓመት ልጅ እንዲህ በማለት ጥያቄ በማቅረብ ላይ ይገኛል፣ “ሳድግ እና ለአቅመ አዳም ስደርስ እኔም እንደ አባቴ ሁሉ ወደ እስር ቤት እጋዛለሁን?“ ሕፃኑ ፍትህ በአሁኑ ጊዜ አጥር የሌለው እስር ቤት ውስጥ እየኖረ መሆኑን ሊገነዘብ አይችልም፡፡
ከጥቂት ሳምንታት በፊት “የኢትዮጵያ የዞን ዘጠኝ ጦማሪዎች” (የፖለቲካ እስረኞችን ከያዘው ከመሀል ከተማ በጥቂት ኪሎ ሜትሮች ርቀት ላይ የሚገኘው የ “መለስ ዜናዊ ታዋቂው የቃሊቲ እስር ቤት” ህንጻዎች ቀጥሎ የተሰየመ) እና ሌሎች ጋዜጠኞች በስም አጥናፍ ብርሀኔ፣ ዘላለም ክብረት፣ በፍቃዱ ኃይሉ፣ አቤል ዋቤላ፣ ማህሌት ፋንታሁን፣ ናትናኤል ፈለቀ፣ አስማማው ኃይለጊዮርጊስ፣ ተስፋለም ወልደየስ እና ኤዶም ካሳዬ የክሱ ጭብጥ ባልታወቀበት ሁኔታ ከህግ አግባብ ውጭ በዘፈቀደ በቁጥጥር ስር ውለው ለእስር ተዳርገዋል፡፡ ፖሊስ በእነዚህ ጦማሪያን እና ጋዜጠኞች ላይ ምን ዓይነት ክስ መመስረት እንዳለበት ገና በመለግ ላይ ይገኛል፡፡
(የገዥው ቡድን ፖሊስ የሚጠረጥረውን ዜጋ በዘፈቀደ በቁጥጥር ስር አውሎ እና እስርቤት በማጎር እያሰቃዬ ተሰራ ለተባለው ጥፋት ማስረጃ እና መረጃ በመፈለግ በዜጎቿላይ ሰብአዊ መብትን በመደፍጠጥ ኢትዮጵያ በዓለም ላይ ብቸኛዋ አገር ናት!!!የይስሙላዎች የዝንጀሮ ፍርድ ቤቶች በዘፈቀደ ከህግ አግባብ ውጭ በቁጥጥር ስርለዋሉት ዜጎች ዋስትና በመንፈግ ፖሊስ እና አቃቤህግ የሚባሉ የገዥው አካልየማጥቂያ መሳሪያ ሎሌዎች የሚፈበረኩ የፈጠራ ውንጀላዎችን አቀነባብረውእስኪያቀርቡ ድረስ የተንዛዙ እና አሰልቺ የሆኑ ማያልቅ ቀጠሮዎችን በመስጠት እናየይስሙላውን ፍርድ ቤት የፍርድ ሂደት ከሚገባው በላይ በማዘግየት በንጹሀን ዜጎችላይ የቁማር ጨዋታ በመጫወት ላይ ይገኛሉ፡፡ በዚህም ምክንያት ነው አነዚህን ፍርድቤቶችን “የይስሙላ የዝንጀሮ ፍርድ ቤቶች እያልኩ የምጠራቸው፡፡” እውነተኛው የዞን ዘጠኝ ጦማሪያን ወንጀል ሀሳብን በነጻ በመግለጽ የሚያምኑበትን ነገር በነጻ ማራመዳቸው እና እነርሱ የተሻለች ኢትዮጵያ በማለት ስለሚጠሯት ኢትዮጵያ ህልም ማለማቸው ነው፡፡ የዞን ዘጠኝ ጦማሪያንን ጉዳይ የሚመለከተው በቅርቡ ቀጠሮ ተይዞለት የነበረው የዳኝነት ችሎት ለህዝቡ እና ጉዳዩን በቅርበት ለሚከታተሉት የዲፕሎማቲክ ማህበረሰብ አባላት ዝግ ነበር፡፡
እስክንድር ነጋን፣ ርዕዮት ዓለሙን፣ ውብሸት ታዬን፣ የዞን ዘጠኝ ጦማሪያንንየሚፈሯቸው ለምንድን ነው?
ናፖሊዮን ቦና ፓርት የተባሉት የፈረንሳይ አምባገነን መሪ በዚያች አገር የነጻው ፕሬስ ላይ ጦርነት ባወጁበት ወቅት “ከአንድ ባታሊዮን ጦር ይልቅ አራት ተቃዋሚ ጋዜጦች የበለጠ ይፈራሉ“ የሚለውን እውነታ የበለጠ ግልጽ አድርጎታል፡፡ ላለፉት 23 ዓመታት በኢትዮጵያ ጫንቃ ላይ እንደ መዥገር በስልጣን ላይ ተጣብቆ ለሚገኘው ገዥ አካል ኤኬ – 47 ከታጠቀ አንድ ባታሊዮን ጦር ይልቅ ብዕር እና የኮምፒውተር ኪይ ቦርድ የያዙ ጥቂት ነጻ ጋዜጠኞች እና ጦማሪያን የበለጠ ያስፈሩታል፣ በፍርሀት ቆፈን ውስጥ እንዲወሸቅ ያደርጉታል፣ ያርዱታል፣ ያስደነብሩታል፣ የሚይዝ የሚጨብጠውን ያሳጡታል፣ የቀን ቅዠት ይፈጥሩበታል፣ በላብ እንዲጠመቅም ያደርጉታል፡፡ በታሪክ መነጽር ሲታይ እና ሲገመገም ሁሉም አምባገነኖች እና ጨቋኞች የነጻውን ፕሬስ የእውቀት እና የክህሎት ኃይል አጥብቀው ይፈሩታል፡፡ በኢትዮጵያ በስልጣን ላይ ተንፈራጥጠው የሚገኙት አምባገነኖች ዘመናዊ የጦር መሳሪያ እስከ አፍንጫው ከታቀው እና በልዩ ልዩ የጦር ክፍሎች ተዋቅሮ በጠላት ላይ ቅጽበታዊ ድልን የመቀዳጀት አቅም ካለው እና የጠላትን ኃይል በማያንሰራራ መልኩ ከሚያደባይ የጦር ኃይል ይልቅ የነጻውን ፕሬስ የዕውቀት እና የክህሎት ኃይል አጥብቀው ይፈራሉ፡፡
ጠቅላላ የብዙሀን መገናኛዎችን እና ነጻውን ፕሬስ መቆጣጠር የገዥዎች እኩይ ምግባር ነው፡፡ የመረጃ ፍሰቶችን በመቆጣጠር በኃይል የሚገዙትን ህዝብ ልብ እና አእምሮ የተቆጣጠሩ እንደሚመስላቸው እምነት አላቸው፡፡ የብዙሀን መገናኛ ዘዴዎችን በመቆጣጠር እንደ በቀቀን እየደጋገሙ ከሚቀፈቅፉት ነጭ ውሸታቸው እውነትን የሚፈበርኩ ይመስላቸዋል፡፡ ነጻውን ፕሬስ አፈር ድሜ በማብላት ሁሉንም ህዝብ ሁልጊዜ ማሞኘት የሚችሉ ይመስላቸዋል፡፡ ሆኖም ግን “እውነት ለዘላለም ተቀብራ እንደማትቀር እና ግፈኞችም በጉልበት ነጥቀው በያዙት የስልጣን ዙፋን ወንበር ላይ ለዘላለም ተጣብቀው እንደማይቆዩበት ድንጋይ በሆነው ልባቸው ያውቁታል፡፡“ ሁልጊዜም ስልጣናቸውን የሚያጡ እየመሰላቸው እለት በእለት የውሸት ድሪቷቸውን እየደረቱ ኑሮ አድርገው ይዘውታል፡፡
በአሁኑ ጊዜ በኢትዮጵያ በስልጣን ወንበር ላይ ተጣብቆ የሚገኘው አረመኔ አምባገነን ገዥ ከብዙ ዓመታት በፊት ናፖሊዮን ተጋፍጦት የነበረውን ዓይነት ሁኔታ ተጋፍጦ ይገኛል፡፡ “ጋዜጠኛ የህዝቡን እሮሮ የሚያሰማ፣ ስህተትን አራሚ፣ ምክርን የሚለግስ፣ የሉዓላዊነት ወኪል እና የአገሮች መምህር ነው፡፡“ ጋዜጠኛ “አገርን የሚያስተምር” ነው፣ መረጃን ለህዝብ የሚሰጥ ነው፣ ህዝቡን በእውቀት የማነጽ እና የማስተማር ኃላፊነት አለው፡፡ እንግዲህ እነዚህ እውነታዎች ነበሩ ናፖሊዮን ነጻውን ፕሬስ እንዲፈሩት ያስገደዳቸው፡፡ የነጻው ፕሬስ ኃይል የናፖሊዮንን አምባገነናዊ አገዛዝ ትርጉም ባለው መልኩ እንደሚያጋልጠው እና በህዝቡ ዘንድ ተጠያቂ እንደሚያደርገው ናፖሊዮን ይገነዘቡ ነበር፡፡ ናፖሊዮን የፈረንሳይን ህዝብ ለማስፈራራት በማሰብ መጠነ ሰፊ የሆነውን የስለላ መረባቸውን በመዘርጋት ሲያካሂዱት የነበረውን ስለላ ሲያጋልጡ የነበሩትን ጋዜጠኞች ለማስፈራራት፣ በእስር ቤት ለማጎር፣ በስራዎቻቸው ላይ ቁጥጥር ለማድረግ እና አንደበታቸውን ለመሸበብ ጊዜ አላባከኑም፡፡ ነጻው ፕሬስ የናፖሊዮን ወታደራዊ እቅድ መክሸፉን አጋልጧል፡፡ ምንም ዓይነት የጦር መሳሪያ ባልታጠቁ ሰላማዊ ዜጎች ላይ ማንንም ሳይለይ በጅምላ በዋና ዋና መንገዶች ላይ የተካሄዱትን ጭፍጨፋዎች እና የእርሳቸው የፖለቲካ ተቀናቃኝ በሆኑት ቡድኖች እና ግለሰቦች ላይ የተካሄደውን እስራት፣ ማሰቃየት እና ግድያ አውግዟል፡፡ በኢትዮጵያ እንደ መዥገር በስልጣን ወንበር ላይ ተጣብቀው የሚገኙት አምባገነኖች በናፖሊዮን ቅዠት በመውደቅ በተመሳሳይ መልኩ ወጣት ጦማሪያንን እና የነጻው ፕሬስ አባላትን ያስራሉ፣ ያሰቃያሉ፡፡ እውነታውን በመፍራት እንቅልፋቸውን አጥተው በነጭ ላብ ተዘፍቀው ያድራሉ!
የኢትዮጵያ ጦማሪያን እና ጋዜጠኞች ልዩ የኢትዮጵያ ጀግናዎች እና ጀግኒቶች ናቸው፡፡ የእውነት ተናጋሪ ተዋጊዎች ናቸው፡፡ አረመኔ አምባገነኖችን በብዕሮቻቸው እና በኮምፒውተር ኪቦርዶቻቸው ይዋጋሉ፡፡ የእነዚህ ወጣቶች ጥይቶች እውነት፣ ቃላት፣ ሀሳቦች፣ እውነታዎች እና እምነቶች ብቻ ናቸው፡፡ የተንሰራፉትን ውሸቶች በእውነት ጎራዴ ይከትፏቸዋል፡፡ መጥፎ እና መሰሪ ሀሳቦችን በጥሩ ሀሳቦች ያሳድዷቸዋል፣ እናም ያረጁ እና ያፈጁ፣ እንዲሁም የጃጁ፣ እና የበከቱ አሮጌ አስተሳሰቦችን በአዲስ እና ተራማጅ በሆኑ አስተሳሰቦች ለመተካት የማስተማር ጥረታቸውን ቀጥለዋል፡፡ የህዝቦችን ተስፋቢስነት በመዋጋት በተስፋ ቃላት ያለመልማሉ፡፡ ፍርሀት በጀግንነት እና በደፋርነት ድል እንደሚመታ ለህዝቡ ያስተምራሉ፡፡ ድንቁርናን እና ኃይለኛ ደንቆሮዎችን በእውቀት እና በምክንያታዊነት ይዋጋሉ፡፡ በእብሪት እና ትእቢት ለተወጠሩት የገዥው አካል አባላት በሰለጠነ መልኩ ለማስተማር እና ለማግባባት ጥረት ያደርጋሉ፡፡ ትዕግስትየለሽነትን በታጋሽነት፣ ጭቆናን ከመሸከም በጽናት ታግሎ በማስወገድ እና በጥርጣሬ ከመሸነፍ በሙሉ እምነት አሳድሮ ድል በመምታት ለመቀየር ይፈልጋሉ፡፡ የህዝቡን ልብ እና አእምሮ ለመያዝ በሚደረገው የትግል አውድ እንደ ወሮበላው የገዥ አካል ስብስብ በተራ የውሸት ፕሮፓጋንዳ እና በኃይል በጉልበት ጨፍልቆ ለመያዝ ሳይሆን እውነታውን እና እውነቱን ብቻ ለወገኖቻቸው በማሳየት በብዕሮቻቸው እና በኮምፒውተር ኪቦርዶቻቸው ይታገላሉ፡፡
ክህደት፣ ውሸት እና ፍርሀት በተንሰራፋባት ምድር ላይ መኖር፣
በኢትዮጵያ ያለው ገዥ አካል እውነት ውሸት በሆነባት፣ እውነት በእየለቱ በምትደመሰስባት እና ሸፍጠኛ አታላዮች በፍርሀት ተዘፍቀው የሚኖሩባት የእራሳቸውን ምድር ፈጥረዋል፡፡ ገዥው አካል እንዲህ የሚለውን የካርቴሲያንን መርህ አዛብቷል፣ “በኛ አስተሳሰብ ብቻ ነገሮች ሁሉ ህልውና ይኖራቸዋል ወይም ደግሞ ህልውና አልባ ይሆናሉ“፡፡ መለስ ዜናዊ የክህደት አለቃ ነበር፡፡ ሁልጊዜ በሱ የማጎሪያ አስር ቤቶች ውስጥ ምንም ዓይነት የፖለቲካ እስረኛ የለም በማለት ሽምጥጥ በማድረግ ይክድ ነበር፣ እንዲህ በማለት፣ “በአሁኑ ጊዜ በኢትዮጵያ ምንም ዓይነት የፖለቲካ እስረኛ የለም፡፡ በእስር ቤት ያሉት አመጸኞች እና አሸባሪዎች ናቸው፡፡ እናም በእስር ቤቶቻችን የፖለቲከ እስረኞች አሉ ብሎ ለመግለጽ አስቸጋሪ ነው የሚሆነው ምክንያቱም የፖለቲካ እስረኞች አይደሉምና፡፡ በሱ የንጉስነት ወቅት ምንም ዓይነት ረሀብ እና ቸነፈር እንዳልነበረ ሙልጭ አድርገው በመካድ እንዲህ ብሎ ነበር፣ በጣም ጥቂት የሆኑ በጣት የሚቆጠሩ በምግብ እጥረት ጉዳት የደረሰባቸው በደቡብ የሀገሪቱ ክፍል በሚገኙ የወረዳ ኪስ ቦታዎች እና በሶማሊ ክልል አካባቢ የአስቸኳይ ጊዜ ሁኔታ ብቻ ነው የነበሩት በማለት ዓይኔን ላፈር ብለዋል፡፡ በአገሪቱ ላይ ተንሰራፍቶ የሚገኘውን ያፈጠጠ እና ያገጠጠ እውነታ ሙልጭ አድርገው በመካድ በኢትዮጵያ ውስጥ ምንም ዓይነት የሰብአዊ መብት ጥሰት የለም“ ብለዋል፡፡ ይህንን ለማስረገጥ በማሰብ እንዲህ ብለው ነበር፣ “ኦጋዴን አካባቢ መንደሮችን አቃጥለዋል እየተባለ ውንጀላ ቀርቦብናል፡፡ ሆኖም ግን በእርግጠኝነት ልነግራችሁ እፈልጋለሁ፤ ኑስ አንድ መንደር እንኳ አልተቃጠለም፡፡ እናም እኔ እስከማውቀው ድረስ አንዲት ጎጆ አልተቃጠለችም፡፡ እኛ እየተከሰስን ያለነው በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎችን ቀድሞ ከነበሩባቸው መንደሮች በማንቀሳቀስ ወደ መጠለያ ካምፖች በማስገባታችን ነው፡፡ በዚህ ጉዳይ ላይ ቅንጣት መረጃ ሊቀርብ አይችልም“ ብሎ ነበር፡፡ የአሜሪካ የሳይንስ እድገት ማህበር/American Association for the Advancement of Science በኦጋዴን መንደሮች ላይ የተካሄደውን የጅምላ የመንደሮች ማቃጠል ወንጀል በሳቴላይት ምስሎች የተረጋገጠው እውነታ ለመለስ ምድር ምናባዊ ህይወት ምንም አይደለም፡፡ አደናጋሪ የፕሬስ ህግ አዋጅ በማውጣት በደርዘን የሚቆጠሩ ምርጥ የኢትዮጵያ ነጻ ጋዜጠኞች እና ጦማሪያን ለእስር እና ግዞት ሲዳረጉ የሌባ አይነ ደረቅ እንዲሉ በሀሰት በነተበው አንደበታቸው መልሰው “ከዓለም የተሻለ ምርጥ የፕሬስ ህግ” በማለት ያደናግራሉ፡፡ እ.ኤ.አ በ2010 የተካሄደውን አገር አቀፋዊ “ምርጫ” ተከትሎ መለስ ፓርቲው ምርጫውን በ99.6 በመቶ ያሸነፈ መሆኑን በኩራት ተናግሮ ነበር፣ ምክንያቱም ህዝቡ ፓርቲያቸውን የሚወደው ስለሆነ ነው በማለት አፋቸውን ሞልተው ተናግረው ነበር፡፡ አቶ መለስ የኦርዌላን/Orwellian የእንስሳት ትረካ ዓይነት እውነታን የሚያራምድ ሰው ነበር፡፡ ውሸቱን ለመንዛት ሲፈልግ “የፖለቲካ ቋንቋን በመጠቀም የለየለትን ነጭ ውሸት እውነት እንዲመስል አድርገው በማቅረብ፣ ግድያ መፈጸም ወንጀል እና የስነምግባር ዝቅጠት መሆኑ ቀርቶ የሚያስከብር እንደሆነ አድርገው በማቅረብ ነጩን ውሸት የእውነት ቅርጽን እንዲላበስ አድርገው በማስመሰል የማቅረብ የባዶ ብልጣብለጥነት አካሄድ መንገድን ይጠቀሙ ነበር፡፡”
በአሁኑ ጊዜ በኢትዮጵያ በስልጣን ወንበር ላይ ተቀምጠው አገሪቱን እያተራመሱ በመግዛት ላይ ስለሚገኙት ስብስቦች አንድ የማይካድ ሀቅ አለ፡፡ ሁሉም በፍርሀት ቆፈን ውስጥ ተወሽቀው ነው እየኖሩ ያሉት፡፡ ያገጠጠውን እና ያፈጠጠውን እውነታ አየፈሩ ነው በመኖር ላይ ያሉት፡፡ የነጻው ፕሬስ ኃይል እውነታውን የሚያጋልጥ ስለሆነ የነጻውን ፕሬስ ኃይል በመፍራት ነው እየኖሩ ያሉት፡፡ በአንድ ወቅት የእነርሱ የአመለካከት ፍልስፍና አለቃ ቁንጮ የነበሩት ቪላድሚር ሌኒን አንዳለው “የመናገር ነጻነት እና የፕሬስ ነጻነት ለምንድን ነው የሚፈቀደው? ለምንድን ነው መንግስት ትክክል ነው ብሎ ያመነበትን ነገር ሲሰራ ትችት እንዲቀርብበት የሚፈቅደው? ተቃዋሚዎችን የጠላት መሳሪያ እንዲሆኑ መንግስት መፍቀድ የለበትም፣ ሀሳቦች ከጠብመንጃ የበለጠ የገዳይነት ባህሪ አላቸው፡፡ ለምንድን ነው ማንም ሰው የማተሚያ ቤት እንዲገዛ እና የሚቀርቡ ሀሳቦችን አትሞ በማሰራጨት በስልጣን ላያ ያለውን መንግስት በተቀነባበረ ስሌት ለመተቸት እና ለማሳፈር እንዲችል የሚፈቀደው?“ ፡፡
እውነታውን በሚገባ ያውቁታል ምክንያቱም እውነታው ህዝቡን ነጻ እንዲሆንያ ደርገዋል፡፡ ነጻነትን ይፈራሉ ምክንያቱም አዲስ ሀሳቦችን ይፈራሉ፡፡ አዲስ ሀሳቦችን ይፈራሉ ምክንያቱም ለውጥን ይፈራሉ፡፡ ነጻ የሆነ ህዝብ የእውነትን ጥሩር ታጥቆ የሀሳብ ነጻነትን ተጎናጽፎ በእራሱ ፈቃድ የእራሱን የመንግስት ዓይነት ለመመስረት ሙሉ ነጻነት አለው፡፡
በኢትዮጵያ ላይ ስላለው ገዥ አካል ያለው እውነታ ምንድን ነው? እውነታው በሰው ልጆች ላይ ግፍን የፈጸሙ ወንጀለኞች ናቸው፡፡ ምንም ዓይነት ህጋዊነት የላቸውም፡፡ በጠብመንጃ ኃይል በጉልበት በስልጣን ወንበር ላይ እንደ መዥገር ተጣብቀው የሚገኙ አምባገነኖች ናቸው፣ ምርጫዎችን በመስረቅ እና በመዝረፍ ተመርጠናል እያሉ በማታለል ተክነዋል፣ በጥልቅ የሙስና ማእበል ውስጥ ተዘፍቀው የአገሪቱን ሀብት በማውደም ላይ ይገኛሉ፣ ስልጣናቸውን በህገወጥ መንገድ በመጠቀም ላይ ይገኛሉ፣ የህግ የበላይነትን በመደፍጠጥ በጫካው ህግ የሚገዙ ህገወጦች ሆነዋል፣ እውነታው ሲታይ በአጠቃላይ በሸፍጥ የታወሩ የጫካውን አስተዳደር ወደ መንግስታዊ አስተዳደርነት አዙረው ህዝብን በማተራመስ ላይ የሚገኙ የስግብግብ ወሮበላ ቡድን ስብሰቦች ናቸው፡፡ እውነታው በአጠቃላይ ሲታይ የአፍሪካን የጨካኝ ዘራፊነት ስርዓት በሀገራችን ላይ የሚተገብሩ ወሮበላ ዘራፊዎች ናቸው፡፡
እነዚህ ወሮበላ ዘራፊዎች ነጻ ጋዜጠኞችን እና ጦማሪያንን ይፈራሉ ምክንያቱም እነዚህ ነጻ ጋዜጠኞች እና ጦማሪዎች አምባገነኖቹ የሚሰሯቸውን ወንጀሎች እና ሙስናዎች፣ የመከኑ እና የወደቁ ፖሊሲዎቻቸውን፣ የአቅም ድሁርነታቸውን እና ድንቁርናቸውን በማጋለጥ እውነታውን ያወጡባቸዋል፡፡ እነዚህ ጭራቃዊ ፍጡሮች በጫማቸው ስር እረግጠው የያዟቸው የግፍ ሰለባዎች ነጻ ቅዱስነት እና የያዙት ጸበል ስለሚያቃዣቸው ነጻ ጋዜጠኞችን እና ጦማሪያንን አጥብቀው ይፈራሉ፡፡ በያዙት ሁሉ ኃይል በመጠቀም እውነቱ ወጥቶ ለህዝብ እንዳይደርስ እና እንዳይታወቅባቸው ማንኛውንም ነገር ከማድረግ ወደ ኋላ አይሉም፡ የሳቴላይት ስርጭቶችን ሳይቀር አፍነዋል፣ የኢንተርኔት ግንኙነቶችን አቋርጠዋል፣ ጋዜጦችን በመዝጋት ጋዜጠኞችን በእየእስር ቤቶች አጉረዋል፡፡ ባለፈው ሳምንት የአረብሳት ለዓለም አቀፉ የግንኙነት ህብረት/International Communication Union እና ለአረብ ሊግ/Arab League ኢትዮጵያ ስርጭቱን ያፈነች መሆኗን እና “ወንጀለኛውን ለመቅጣት አስፈላጊው እርምጃ እንዲወሰድ” እና በዚህ ህገወጥ ድርጊት ምክንያት ለደረሰው ጉዳት ወይም በዚህ ህገወጥ የአፈና ተግባር ምክንያት ወደፊት ለሚደርስ ማንኛውም አደጋ ተገቢውን ካሳ እንድትከፍል እንዲደረግ ተማጽዕኖውን አቅርቧል፡፡ በአሁኑ ጊዜ ገዥው አካል በገበያ ላይ የቀሩትን እና በገዥው አካል ላይ ጠንካራ ጥችት የሚያቀርቡትን ጥቂት ጋዜጦች በየመንገዶች እያዞሩ የሚሸጡትን ጋዜጣ አዟሪዎችን እያሳደደ፣ እያስፈራራ እና በቁጥጥር ስር እያዋለ ይገኛል፡፡
እውነታው በኢትዮጵያ ሀሳብን በነጻ ከመግለጽ ጉዳይ ጋር በተያያዘ መልኩ እየተካሄደ ላለው ጭቆና እና አፈና የቻይናዎች ስውር እጆች ያሉበት መሆኑ ነው፡፡ ቻይናዎች ለገዥው አካል የማፈኛ የቴክኖሎጂ መሳሪያዎችን ማቅረብ ብቻ አይደለም የሚያከናውኑት፡፡ ሆኖም ግን ለተንቀሳቃሽ ስልኮች እና ለኢንተርኔት አገልግሎት የመሰረተ ልማት ስራዎችም ግንባር ቀደም ተዋንያን ናቸው፡፡ የመረጃ ፍሰት ከኢትዮጵያ እንዳይወጣ እና ወደ ኢትዮጵያም እንዳይገባ ለመገደብ እና ለማቋረጥ የአንድ መስኮት ፈጣን የአግልግሎት መስጫ ኪቶችን ይዘዋል፡፡ ከዛሬ ሁለት ዓመታት ገደማ በፊት የቀድሞዋ የዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር የነበሩት ሄላሪ ክሊንተን ዛምቢያን በመጎብኘት ላይ ሳሉ የቻይናውያን በአፍሪካ አህጉር ላይ ያላቸውን ሚና በማስመልከት እንዲህ ብለው ነበር፣ “በቅኝ ግዛት ዘመን ጊዜ መምጣት እና ለመሪዎቹ ገንዘብ በመስጠት የተፈጥሮ ሀብቶችን ከአፍሪካ መውሰድ ቀላል ነበር፣ በምትለቅቅበት ጊዜ እዚህ ላለው ህዝብ ምንም ነገር ትተህ አትወጣም፣ በአሁኑ ጊዜ አዲስ ቅኝ ተገዥነት በአፍሪካ ማየት አንፈልግም“ ብለው ነበር፡፡ እውነታው ግን ቻይናውያን በኢትዮጵያ መቆየታቸው እና የእጅ አዙር ቅኝ ግዛት መያዛቸው ብቻ ሳይሆን ለገዥው አካል የቴክኒክ እገዛ በመስጠት፣ የኦዲዮ እና ቪዲዮ መሳሪያዎችን በማቅረብ የመረጃ ምርመራ በማድረግ እና በኤሌክትሮኒክ መገናኛ ብዙሀን ላይ አፈናዎችን በማካሄድ ነጻ አሰተሳሰብን በመጨቆን በዋናነት ተጠያቂዎች ናቸው፡፡
ነጻነትን ይፈራሉ፡፡ ነጻነት ምንድን ነው? የሁሉም የሰው ልጆች ነጻነቶች ባህሪያት ከፍርህት የሚገኙ ነጻነቶች ናቸው፡፡ በተግባራዊ ሁኔታ ሲታይ አንድ ሰው ያሰበውን ለመናገር መፍራት ወይም ደግሞ አንድ ሰው ደስ ያለውን መጻፍ መፍራት ወይም በአንድ ሀሳብ ማለትም ሀይማኖት ወይም ፍልስፍና ላይ ማመን እና አለማመንን መፍራት ወይም ደግሞ አንድ ሰው ከመረጠው ሰው ጋር አብሮ መገናኘት መፍራት ማለት አይደለም፡፡ ዋናው እና የመጨረሻው የሰው ልጅ ሁሉ ሊያደርገው የሚገባው ህዝቡ እራሱ ስልጣን የሰጣቸው በስልጣን ወንበር ላይ ያሉት ሰዎች ናቸው በህብረተሰቡ የኑሮ ሂደት ላይ መፍራት እና ህዝቡን ማክበር ያለባቸው፡፡
ሀሳብን ይፈራሉ፡፡ “ሀሳቦች ከጠብመንጃ የበለጠ ገዳዮች ናቸው“ በማለት ሌኒን አስጠንቅቀዋል፡፡ ሀሳቦች ሳይንስን፣ ፖለቲካን እና ማናቸውንም የሰው ልጅ የሚያደርጋቸውን እንቅስቃሴዎች ሁሉ የመለወጥ ኃይል አላቸው፡፡ ከምንም በላይ ዓለም ጠፍጣፋ አይደለችም፡፡ ሆኖም ግን በኢትዮጵያ ያሉ ገዥዎች የአዲስ ጠፍጣፋ መሬት ባለቤቶች ናቸው፡፡ እንደ ጥንቱ ንጉሶች፣ ዛሮች፣ እና ማሃራጃሆዎች ሆነው ከህዝቡ ፈቃድ ውጭ ( በተሰረቀ ስምምነት) መሰረት መግዛት ይፈልጋሉ፡፡ ጥቂት ሞራላዊ ጠቀሜታ ያላቸው ሀሳቦች ሲኖሯቸው ነገሮችን በቀላሉ ለመገንዘብ እና አዳዲስ ሀሳቦችንም ለማድነቅ እና ተቀብሎ ወደ ተግባር ለማዋል የምሁርነት አቅሙ የሌላቸው የመንፈስ የአስተሳሰብ ድሁሮች ናቸው፡፡ ሆኖም ግን የጎሳ ክፍፍልን ለማራመድ፣ ስግብግብነት እና ጥላቻን ለማምጣት፣ የጥላቻ ከባቢን የመፍጠር፣ ግጭትን የመጫር፣ ሙስናን ለማስፋፋት እና ለማጠናከር፣ ህብረትን በመናድና የጥላቻ መንፈስን በመዝራት እንዲሁም በሰዎች መካከል ጥርጣሬ እና አለመተማመን እንዲነግስ በማድረግ ጭንቅላቶቻቸው ዋና የዲያብሎሳዊነት ቤተሙከራዎች ናቸው፡፡ ህዝብን ሊያስተባብሩ እና ሊያፋቅሩ የሚችሉ ሀሳቦችን ለማመንጨት፣ በጎሳዎች መካከል ፍቅርን የማስፈን፣ ብሄራዊ አንድነትን የማምጣት፣ የጋራ መግባባትን የመፍጠር፣ የጓዳዊነት መንፈስ የማጠናከር እና እምነትን የማራመድ አቅመቢሶች ናቸው፡፡
አዳዲስ ሀሳቦችን የሚፈሩ በኢትዮጵያ በስልጣን ወንበር ላይ ተቆናጥጠው የሚገኙ አምባገነኖች የአዲስ ሀሳብ አመንጭ እና ባለራዕይ መስለው ለመታየት ይሞክራሉ፡፡ ህዝቡ እና ዓለም ወደፊት ጥሩ ነገር የሚያስቡ መልካም ነገር አላሚዎችና ፈጣሪዎች እንደሆኑ አድርጎ እንዲመለከታቸው እና እምነት እንዲኖረው ይፈልጋሉ፡፡ ሆኖም ግን በህልም የቅዠት ፍርሀት ተዘፍቆ ያለ ማንም ሰው መልካም አላሚ ሊሆን አይችልም፡፡ ባለራዕይ መሪዎች ለሚያደርጓቸው ማለትም ታማኝነት፣ ኃላፊነትነትን የመሸከም ብቃት፣ ሌሎችን አነቃቅቶ እና አሳምኖ በስራ የማሳተፍ ችሎታ፣ ያለፉትን ስህተቶች በግዴለሽነት እንዳሉ ከመድገም ይልቅ ከስህተት እና ከውድቀት መማርን፣ ስህተት በሚሰሩበት ጊዜ ይቅርታ አድርጉልኝ ብሎ መጠየቅን፣ ግልጽነት፣ ትክክለኛውን ነገር ለመስራት ፍትሀዊነት እና በፍቅር ላይ የተመሰረተ ሆኖ ከመገኘት ተግባራት ጋር ሁሉ አይተዋወቁም፡፡ መጥፎ እና ዕኩይ ተግባራትን ለማድረግ ፍቅር ያላቸው መሰሪ መሪዎች ናቸው፡፡ ኪሶቻቸውን የሚወጥሩትን የተዘረፉ በርካታ ገንዘቦችን ዓይኖቻቸው በቀላሉ ማየት ይችላሉ፡፡ ሆኖም ግን አሁን እየፈጸሟቸው ያሏቸው በርካታ ወንጀሎች በዘለቂነት ለወደፊት ሊያስከትሉት የሚችሏቸውን እንደምታዎች ለማየት የታወሩ ናቸው፡፡ ጠንካራን ሀሳብ ጊዜው እየመጣ ያለውን ሀሳብ የሚያቆመው ምድራዊ ኃይል የለም፡፡ የኢትዮጵያ ህዝብ ለነጻነት የሚያደርገውን ተጋድሎ የሚያቆመው ኃይል የለም፡፡ አንዴ ከተጀመረ በመንገዱ ላይ ያለውን ጋሬጣ ሁሉ እየጠራረገ ወደፊት ይገሰግሳል፡፡
ለውጥን ይፈራሉ፡፡ ለውጥ ምንድን ነው? ለውጥ በሁሉም ነገር የሚከሰተውን የዕድገት እና የመበስበስ ዓለም አቀፋዊ ዘላለማዊ የለውጥ ህግ የሚገዛ ሂደት ነው፡፡ በኢትዮጵያ በስልጣን ላይ ያለው ገዥ አካል ለውጥን አጥብቆ ይፈራል ምክንያቱም በህበረተሰቡ ላይ ያላቸውን የኢኮኖሚ እና የፖሎቲካ የበላይነት ቦታ ስለሚያሳጣቸው ነው፡፡ ለውጥን ሊያመጡ የሚችሉ ነገሮችን በሰላማዊ መንገድ ለውጥ ለማምጣት የሚንቀሳቀሱትን ማናቸውንም ሙከራ ሁሉ ይደመስሳሉ፡፡ ከዚህ አንጻር “በሰላማዊ መንገድ የለውጥ አብዮት እንዳይመጣ የሚከለክሉ ሁሉ የአመጽ ለውጥ በኃይል እንዲመጣ ይገደዳሉ“ የሚለውን ሀቅ ለመገንዘብ የተሳናቸው ይመስላል፡፡
በፖለቲካ ህጋዊነት ማጣት እና በመንግስት አቅም ማጣት ምክንያት ኢትዮጵያ በአሁኑ ጊዜ በፖለቲካ መበስበስ የመጨረሻ ጠርዝ ላይ ያለችበት ሁኔታ ነው የሚታየው፡፡ የጨነገፈ መንግስት ሆናለች፡፡ ባለፉት ሩብ ምዕተ ዓመታት የጎሳ ክፍፍል ፖሊሲ (የጎሳ ፌዴራሊዝም) “ልማታዊ መንግስት” ባለሁለት አሀዝ የኢኮኖሚ እድገት አስመዘገብን በማለት የሚራገበው እርባናየለሽ ፕሮፓጋንዳ ቢኖርም እንኳ ኢትዮጵያን በሁለት አማራጮች ላይ ጥሏታል፡፡ የእነርሱ ነጭ ውሸት ብቻ ነው በባሁለት እና በባለሶስት አሀዝ እድገት ያስመዘገበው፡፡
ኢትዮጵያ በአሁኑ ጊዜ በመስቀለኛ መንገድ ላይ ቆማለች፡፡ እንደተባበረች ሀገር አንድ ሆና ወደፊት ትገሰግሳለች ወይም ደግሞ ወደተለያዩ ትናንሽ የተበጣጠሱ ክልሎች ትገነጣጠላለች፡፡ የአፓርታይድ ዓይነት ባንቱስታንስ በኢትዮጵያ ክልል እየተባለ በዘር እና በቋንቋ የተቀየደ የአገዛዝ ስርዓት ነው፡፡ ኢትዮጵያ የተበጣጠሱ ግዛቶች ስብስብ የምትሆን ከሆነ የመጀመሪያው ቸግር ቀማሽ የሚሆኑት አሁን በስልጣን ላይ ተጣብቆ የሚገኘው ገዥው አካል፣ የእነርሱ ጋሻጃግሬዎች እና ደጋፊዎች ናቸው፡፡ በፖቲካ ስልጣን ማጣት ብቻ የሚቆም ሳይሆን ቢያንስ እስከ አሁን ድረስ በአገር ውስጥ የሚደረግ ለውጥ ዘግይቶ እንደደረሰ ባቡር ይቆጠራል፡፡ በምስራቅ አውሮፓ በመካከለኛው ምስራቅ ሲነፍስ የነበረው የለውጥ ነፋስ ያለምንም ጥርጥር በኢትዮጵያም መንፈሱ የማይቀር ጉዳይ ነው፡፡ ሊነሳ የሚችለው ብቸኛ ጥያቄ ግን እነዚህ ነፋሶች ተስማሚ እና በሰላም የሚያልፉ ወይስ ደግሞ ሁሉንም ነገር እየገነደሱ እና እየቦደሱ የሚጥሉ ኃይለኛ የሁሪኬን/hurricane-force ሞገዶች ይሆናሉ የሚለው ነው፡፡
እውነት ነጻ ያወጣሀል ነጻ አስከሆንክ ድረስ ሆኖም ግን ነጻ ያልሆኑት ይሰቃያሉ፣
“እውነት ነፃ ታወጣሀለች” ተብሎ ተጽፏል፡፡ ነጻነት እና ፍርሀት ለእየራሳቸው ተነጥለው የሚኖሩ ናቸው፡፡ የነጻው ፕሬስ እና ጦማሪያን ብቸኛው ተግባራቸው እንዳዩት እውነታውን ወዲያውኑ መናገር ነው፡፡ ስለ እውነታው ያላቸውን ሀሳብ የለምንም ፍርሀት የመግለጽ ነጻነት አላቸው፡፡ ሆኖም ግን ህዝቡ እውነታውን ቀድሞም ቢሆን ያውቀዋል፡፡ ኢትዮጵያ በባለሁለት አሀዝ የኢኮኖሚ እድገት አስመዝግባለች የሚለው ነጭ ውሸት ቢሆንም ህዝቦች እውነታውን ያውቁታል፡፡ የሚበላ በቂ ምግብ እንደሌለ ያውቃሉ፣ እናም ሚሊዮኖች በየቀኑ እየተራቡ እንዳሉ ያውቃሉ፡፡ እንዲሁም በቂ የውኃ አገልግሎት ወይም የኤሌክትሪክ ኃይል እንደሌለ ያውቃሉ፡፡ አናሳ የህክምና አገልግሎት ነው እየተሰጠ ያለው፣ ወጣቶች ጥራት ያለው ትምህርት አያገኙም እናም ስራ አጦች ናቸው፡፡ ገዥው አካል በሙስና ማጥ ውስጥ የተዘፈቀ እና የበከተ ነው፣ እንዲሁም በሰው ልጆች ላይ ወንጀልን ይፈጽማል፡፡ ህዝቦች በግልጽ የአየር ድባብ ውስጥ እስረኛ ሆነው እንደሚኖሩ ያውቃሉ፡፡
የነጻ ጋዜጠኞች እና የጦማሪዎች ወንጀል የሚያውቁትን ነገር ለማያውቁት ወገኖቻቸው መግለጻቸው ብቻ ነው፡፡ የእነርሱ ወንጀል የማዕድን ሙስና እና ስልጣንን ከህግ አግባብ ውጭ መጠቀምን፣ እንዲሁም በሰው ልጆች ላይ የሚፈጸሙትን ወንጀሎች እየቆፈሩ በማውጣት ማስረጃ በማቅረባቸው ነው፡፡ ለዚህም በስልጣን ላያ ያለው ገዥ አካል እየፈራቸው ያለው፡፡ ገዥው አካል እውነታው ሳይታወቅ ተቀብሮ እንዲቀር እና እንዲረሳ ይፈልጋል፡፡ ገዥው አካል እውነታው እንዳይታወቅ በመደበቅ፣ እውነት ተናጋሪዎችንም ጸጥ በማስደረግ እና በየእስር ቤቶች በማጎር ለዘላለም ጸጥ በማድረግ ትንፍሽ እንዳይሉ በማድረግ እውነትን የመግደል እምነት አለው፡፡ ጆርጅ ኦርዌል እንደጠቆሙት፣ ”የማጨበርበር እና የሀሰት ሸፍጥ በተንሰራፋበት ጊዜ እውነትን መናገር አብዮተኛነት ድርጊት ነው“ ብለው ነበር፡፡ በአሁኑ ጊዜ የኢትዮጵያ ጦማሪያን የኢትዮጵያ የማይበገሩ አብዮተኞች ናቸው፡፡
ፍርሀትን በብዙሀን መገናኛ እንደ መሳሪያ መጠቀም፣
በስልጣን ላይ ያለው ገዥ አካል ከብዙ ጊዜ ጀምሮ ዋና ድክመትን እንደ ትልቅ መጠቀሚያ መሳሪያ አድርጎ ይጠቀምበታል፡፡ ህዝብን ግራ ለማጋባት፣ እርስ በእርስ ለመከፋፈል፣ ለማታለል፣ ጥላሸት ለመቀባት እና ሀሳብን ከዋናው ጉዳይ አቅጣጫውን ለማስቀየስ ፍርሀትን በዋና መሳሪያነት ይጠቀምበታል፡፡ ማቋረጫ የሌለው የፍርሀት ዘመቻ በህብረተሰቡ ላይ ለመንዛት ሲፈልግ፣ ጥላሸት ለመቀባት እና ለማጠልሸት ሲፈልግ በህዝብ የግብር መዋጮ የሚተዳደረውን መገናኛ ብዙሀን ለእኩይ ምግባር ሌት ቀን ይጠቀማል፡፡ ገዥውን አካል የሚቃወሙትን ቡድኖች እና ግለሰቦች ጸጥ ለማድረግ ሲፈልግ እርባናየለሽ በውሸት ላይ ተመስርተው የተቀነባበሩ ዘጋቢ ፊልሞችን በመፈብረክ “አሸባሪ” የሚል ታፔላ በመለጠፍ በአሰልችው የመገናኛ ብዙሀን እንደበቀቀን ይደጋግማቸዋል፡፡ የውሸት ሸፍጥ በታጨቀበት እና ለመስማት እና ለማየትም አስቀያሚ በሆነው “አኬልዳማ” ብሎ በሰየመው ለምንም የማይውል እርባናየለሽ ዘጋቢ ፊልም ኢትዮጵያ በዲያስፖራው ተቃዋሚ ኃይል እና በአገር ውስጥ ባሉ የእነርሱ የግብር ተመሳሳዮች አማካይነት እንዲሁም ሌሎች አሸባሪ ቡድኖች ትብብር እና ርብርብ አደገኛ የሽብር አደጋ ተደቅኖባት እንደሚገኝ አደንቋሪ ጩኸታቸውን አሰምተዋል፡፡ “አኬልዳማ” በዓለም ላይ የተደረጉትን በጣም አስፈሪ እና አስቀያሚ ምስሎችን ሁሉ ለቃቅሞ በቪዲዮ በማሳየት በቅርቡ በህይወት የተለዩት አቶ መለስ ዜናዊ ተቃዋሚዎቻቸውን ጥላሸት በመቀባትና በሶማሌ የሚንቀሳቀሰው የአልቃይዳ እና አልሻባብ ቅጥረኞች ናቸው ብለው በአሸባሪነት በመፈረጅ የጥቃት ብቀላቸውን በንጹሁነ ዜጎች ላይ በሰፊው ተግብረውታል፡፡
በሌላ “ጅሃዳዊ ሀራካት” በተባለ እርባናየለሽ ዘጋቢ ፊልም በክርስቲያን እና በሙስሊሙ ህብረተሰብ መካከል ፍርሀት እና ጥላቻን ለማስፋፋት በማሰብ ጸረ እስልምና እሳትን የመጫር ሙከራ አድርገው በህዝቡ አርቆ አስተዋይነት እና የንቃት ደረጃ ምክንያት እኩይ ምግባራቸው ሳይሳካ መክኖ ቀርቷል፡፡ ለዘመናት አብሮ እና ተከባብሮ እየኖረ ያለውን የክርስቲያን እና የሙሰሊም ማህበረሰቡን በማጋጨት የእስልምና አሸባሪዎች በድብቅ ጅሀዳዊ መንግስት ለመመስረት ዕቅድ አውጥተው ተንቀሳቅሰዋል በማለት በሁለቱ ታላላቅ ኃይማኖቶች እምነት ተከታዮች መካከል የማያባራ እልቂት እና የደም ጎርፍን ለማዝነብ የታቀደ ዲያብሎሳዊ የድርጊት ዕቅድ ነድፈው ነበር፡፡ አሁንም ህዝቡ የነቃባቸው እና ከእነርሱ እኩይ አስተሳሰብ ውጭ የመጠቀ ሀሳብ ስላለው እና ስላወቀባቸው ዕቅዳቸው አሁንም መክኖ ቀርቷል፡፡
ፍርሀት እና ጥላቻን በህዝቡ ውስጥ ለማስፋፋት እና ምናባዊ የሆነ የዘር እና የጎሳ እልቂት እንዲሁም የኃይማኖት ጽንፈኝነት እልቂት እንደሚከሰት በመስበክ ይህንንም እልቂት ለማስወገድ ብቸኛ ቅዱሶች እነርሱ እንደሆኑ አድርገው በማቅረብ እና በማደናገር ጸረ ኢትዮጵያ እና ዘረኛ አስተሳሰብ የተጠናወታቸው ጎጠኞች መሆናቸውን በአደባባይ አስመስክረዋል፡፡ አሁንም ተስፋ ባለመቁረጥ አንዱን ጎሳ በሌላው ላይ በማስነሳት ለማጋጨት ሌት ቀን በመስራት ላይ ይገኛሉ፡፡ “የጎሳ ፌዴራሊዝም/ethnic federalism” በሚል እኩይ ስልት የዘር ማጽዳት ዘመቻቸውን ቀጥለውበታል፡፡ የጎሳ ጥላቻን ለመቀስቀስ ታሪካዊ ብሶቶችን እየፈበረኩ እና ጥቃቅን ነገሮችን እያጋነኑ በህዝቡ ዘንድ አለመተማመን እና ግጭቶች እንዲነሱ አበርትተው በመስራት ላይ ይገኛሉ፡፡ ህዝቡ ግን ስለነቃባቸው በባዶነታቸው ቀልበቢስ በመሆን እንደ አበደ ውሻ ከወዲያ ወዲህ በመቅበዝበዝ ላይ ይገኛሉ፡፡ የእራሳቸውን ፍርሀት እንደ መሳሪያ በመጠቀም ህዝቡን ለማደናገር ይሞክራሉ፡፡
በኢትዮጵያ ትንታግ ጋዜጠኞች እና ጦማሪያን ላይ የተከፈተው ጦርነት በእራሷ በእውነት ላይ የተከፈተ ጦርነት ነው፣
በኢትዮጵያ በስልጣን ላይ እንደ መዥገር ተጣብቆ የሚገኘው ገዥ አካል በነጻው ፕሬስ ጋዜጠኞች እና በጦማሪያን ላይ ያወጀው ጦርነት በእውነት በእራሷ ላይ ያወጀው ጦርነት ነው፡፡ ገዥው አካል ላለፉት ሩብ ምዕተ ዓመታት በተደረጉት ጦርነነቶች እና ግጭቶች ሁሉ በድል አድራጊነት ተወጥቷል፡፡ ሆኖም ግን በአሁኑ ጊዜ ጎራዴ እና ኤኬ 47 አውቶማቲክ ጠብመንጃዎችን በታጠቁ አምባገነኖች እና ብዕሮች እና የኮምፒውተር ኪቦርዶችን በሚጠቀሙ ጋዜጠኞች እና ጦማሪያን መካከል የሚደረገው ወሳኙ ፍልሚያ ተቃርቧል፡፡ ያ ጦርነት እና ፍልሚያ በኢትዮጵያውያን/ት ልብ እና አእምሮ ውስጥ ሰርጾ ሁሉንም ዜጎች ለወሳኙ ፍልሚያ እና ለድል ጉዞ ጥርጊያ መንገዱን የሚያመቻች ይሆናል፡፡ የዚያ ጦርነት እና ፍልሚያ ውጤቱ ምንም ይሁን ምን በእርግጠኝነት የምናገረው ነገር ቢኖር ፍልሚያው የሀገሪቱን የወደፊት ዕጣ ፈንታ የሚወስን ይሆናል፡፡ በእርግጥ ያ ጦርነት በእውነት አራማጅ ወገኖች አሸናፊነት እንደተደመደመ እምነት አለኝ፡፡ ኤድዋርድ ቡልዌር ሊቶን የተባሉት ገጣሚ በትክክል እንዳስቀመጡት ጎራዴ በታጠቁት እና ብዕርን በጨበጡት ተዋጊዎች መካከል በሚደረግ የጦርነት ፍልሚያ በመጨረሻ ሁልጊዜ የወሳኙ ድል ባለቤት የሚሆኑት ብዕርን የጨበጡት ናቸው፡፡
እውነትን ጨብጠዋልና!
እውነት፣ ይህ!
ከሰዎች አገዛዝ ስር ሌላ ታላቅ ነገር አለ፣
ብዕር ከጎራዴ የበለጠ ኃይል አለው፡፡ አስተውል/ይ
ቀስት ተሸካሚዎች ይፈነድቃሉ፣ ግን ምንም የሚመጣ ነገር የለም!-
ልዩ ታምር ከጌታቸው እጀ ይቀበላሉ፣
እናም ቄሳሮችን በድን ለማድረግ ያምጻሉ
ታላቋ መሬት ትንፋሽ ያጥራታል!- ጎራዴውን ከዚህ ወዲያ ውሰዱ-
መንግስታት ከእርሱ ውጭ ሊጠበቁ ይችላሉና!
ሆኖም ግን በኢትዮጵያ ያለውን ገዥ አካል ማዳን ወይስ ደግሞ የኢትዮጵያን ነጻ ፕሬስ እና ጦማሪያንን ማዳን የሚል ወሳኝ ጥያቄ ቢቀርብልኝ ቶማስ ጃፈርሰን እንደመረጡት ሁሉ እኔም የኋለኛውን ማዳን የሚለው እንዲጠበቅልኝ እመርጣለሁ፡፡ ቶማስ ጃፈርሰን እንዲህ የሚል ጥያቄ ቀርቦላቸው የሚከተለውን መልስ ሰጥተው ነበር፣ ”የእኛ መንግስት መሰረቱ የህዝብ ሀሳብ እንደመሆኑ መጠን የመጀመሪያው ዓላማ መሆን ያለበት ያንን መብት ማስከበር ነው፡፡ እናም ጋዜጦች የሌሉበት መንግስት ከሚኖር ወይም ደግሞ መንግስት በሌለበት ጋዜጦች ብቻ ከሚኖሩ የትኛው የተሻለ ነው የሚል ምርጫ ቢቀርብልኝ የኋለኛውን ለመምረጥ ለሰከንድ እንኳ ጥርጣሬ አይኖረኝም፡፡ ሆኖም ግን ይህን ስል ማንኛውም ሰው እነዚህን ጋዜጦች መቀበል እና ማንበብ መቻል አለበት፡፡“
በተመሳሳይ መልኩ ለእኔም ነጻ ጋዜጠኞች እና ጦማሪያን የሌሉበት ገዥ አካል ከሚኖር ወይም ደግሞ ገዥ አካል በሌለበት ነጻ ጋዜጠኞች እና ጦማሪያን ብቻ ከሚኖሩ የትኛው የተሻለ ነው የሚል ምርጫ ቢቀርብልኝ የኋለኛውን ለመምረጥ ለሰከንድ እንኳ ጥርጣሬ አይኖረኝም፡፡ ከሁሉም በላይ ለዓላማ በጽናት የቆምኩ፣ ለምሰራው ትክክለኛ ስራ ሁሉ ኩራት የሚሰማኝ፣ ላመንኩበት ዓላማ ከልብ እና በወኔ የቆምኩ፣ ዓላማየን ለማስፈጸም በከባድ እርምጃ ወደፊት የምገሰግስ፣ ላልሰራሁት ወንጀል ይቅርታን የማልጠይቅ፣ በምሰራው ስራ ሁሉ የማላፍር፣ ቆራጥ እና የማያወላውል ባህሪን የተላበስኩ የኢትዮጵያ ጦማሪ ነኝ!!!
ኃይል ለነጻ ጋዜጠኞች እና የኢትዮጵያ ጦማሪያን!
ውድቀት እና ዉርደት ህዘብን በጠብመንጃ ኃይል አስገድደው ለመግዛት ለተነሱ የዕኩይ ምግባር አራማጆች!
ኢትዮጵያ በክብር ለዘላለም ትኑር!

ኦባንግ “ከምርጫው” በፊት ለተቃዋሚዎች “ምርጫ” አቀረቡ

$
0
0

Obang Methoለአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ (አኢጋን) ዋና ዳይሬክተር አቶ ኦባንግ ሜቶ በአገር ውስጥ ለሚገኙ የተቃዋሚ ፖለቲካ ፓርቲዎችና አግባብ አላቸው ለሚሏቸው አካላት በኢትዮጵያ ወቅታዊ ጉዳይ ላይ ተቀምጠው እንዲመክሩ ማሳሰቢያ ሰጡ፡፡ ኢህአዴግ በውስጥ ችግሩ፣ በውጭ ተጽዕኖ ወይም በፖለቲካው የተፈጥሮ ባህርይ የሚከስምበት ደረጃ መድረሱን ያሳሰበው በ”ጥቁሩ ሰው” ኦባንግ ስምና ፊርማ የተበተነው የአኢጋን ደብዳቤ፤ የተቃዋሚ ፓርቲዎች ልዩነታቸውን አጥብበው እንዲሠሩ ጠይቋል፡፡ ይህንን ለኢትዮጵያና ለሕዝባቸው ሲሉ መሥራት የማይችሉ ከሆነ ከኢህአዴግ በላይ ተጠያቂ ሊሆኑ እንደሚችሉ አስጠንቅቋል፡፡

የፖለቲካ ዕርቅ በመጀመሪያ በተቃዋሚዎች ደጅ ሊተገበር እንደሚገባው ያሳሰበው አኢጋን፤ ይህንኑ ዕርቅ መሠረት በማድረግ ወደ ኅብረት እንዲመጡ በደብዳቤው ገልጾዋል፡፡ ወደ ኅብረት ሲመጡ የፖለቲካ ሥልጣን የመጨበጥ ዓላማቸውን ወደ ጎን መተው እንዳለባቸውና ኢትዮጵያን በማዳን ተግባር ላይ እንዲያተኩሩ በጥብቅ አሳስቧል፡፡

መግለጫው ሲቀጥልም “የጋራ ንቅናቄያችን ከበርካታ ዓለምአቀፋዊ ድርጅቶችና ታዋቂ ግለሰቦች ጋር ካለው ግንኙነት አኳያ በኢትዮጵያ ጉዳይ ላይ መረጃ ይሰበስባል፡፡ በቅርቡ አንድ ታዋቂ የምዕራቡ ዓለም የፖሊሲ አውጪ ሲናገሩ ኢትዮጵያውያን የምዕራቡ ዓለም ነጻ ያወጣናል ብለውበጭራሽ ማመን የለባቸውም፡፡ ከውጭ ሚላከውን ዕርዳታና ድጋፍ ብናቆም እንኳን ይህ ሚሆን አይደለም፡፡ የለውጥ አራማጅና መሪመሆን ለባቸው ኢትዮጵያውያን ራሳቸው ናቸው እንጂ ለጋሽ መንግሥታት አይደሉም፡፡ ኢትዮጵያውያን ይህንን ሊረዱ ይገባል፡፡ኢትዮጵያውያን ራሳቸው ከህወሃት/ኢህአዴግ የተሻለ አማራጭ በሚፈጥሩበት ጊዜ እኛ የግድ እንድንደግፋቸው ያደርጉናል በማለት ለጋራ ንቅናቄያችን ምስክርነታቸውን ሰጥተዋል” በማለት በመረጃ ላይ የተደገፈ ጭብጥ አቅርቧል፡፡

ሰሞኑን የዚህ ዓመት የSEED ተሸላሚ የሆኑት ይህ የአቶ ኦባንግ የምርጫ አማራጭ ግልጽ ደብዳቤ መጪውን ሁኔታ በሚከተለው ሁኔታ ገልጾታል፤ “አገራችን በበርካታ ድሎች ያንጸባረቀ ታሪክ ያላት ነች፡፡ ከሁሉ በበላይ የሚጠቀሰው የዓድዋ ድል ድጋሚ የሚፈጸምበት ጊዜቢኖር አሁን ነው፡፡ የዓድዋን የጦር ድል በፖለቲካው መድረክ እንድገመው፡፡ መጪውን ምርጫ ፖለቲካዊ የዓድዋ ድልየምንጎናጸፍበት እናድርገው፡፡ ነጻነታችን እንደ ዕርዳታ እህ ከምዕራባውያን የሚለገሰን አይደለም፡፡ ስለዚህ እኛው ራሳችን እንደአድዋ ድል አንድ ሕዝብ ሆነ በመውጣት የራሳችን የምናደርገበት ጊዜ አሁን ነው፡፡ ቅንነት ካለ የጦር ሜዳውን አድዋ በፖለቲካውሜዳ ላይ መድገም ይቻላል፡፡ አንድ ሊያደርጉን ሊያስተባብሩን የሚችሉ “ምኒልኮችን” ለመጠቀም ፈቃደኛና ቅን እንሁን፡፡

በአኢጋን አድራሻና በዋና ዳይሬክተሩ አቶ ኦባንግ ሜቶ ስምና ፊርማ የተሰራጨው ይህ የማሳሰቢያ ግልጽ ደብዳቤ አኢጋን በተለይ በዕርቅ ዙሪያ የሚጠየቀውን ማንኛውንም ጥያቄ ድጋፍ እንደሚሰጥ ያረጋገጠ ነው፡፡ የደብዳቤው ሙሉ ቃል ከዚህ እንደሚከተለው ቀርቧል፡፡


“ነጻነትነታችን እንደ ዕርዳታ እህል ከምዕራባውያን የሚለገሰን አይደለም!”

ለአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ በኢትዮጵያ ለሚገኙ የፖለቲካ መሪዎች ያስተላለፈው ግልጽ መልዕክት

የተወደዳችሁ በኢትዮጵያ የምትገኙ የፖለቲካ ፓርቲ መሪዎች፤

በቅድሚያ ለአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ (አኢጋን) የአክብሮት ሰላምታ በማቅረብ በትግሉ መስክ የምትከፍሉትን መስዋዕትነት የሚያደንቅ መሆኑን ይገልጻል፡፡ በተለይ በአሁኑ ጊዜ የፖለቲካ ምህዳሩ እጅግ ጠብቦ የለም የሚባልበት ደረጃ በደረሰበት ወቅት በምታገኙት ስንጥቅ ሁሉ እየተጠቀማችሁ ለህዝባችሁ የብርሃን ጭላንጭል ስለምትፈነጥቁ አኢጋን ሥራችሁን ያደንቃል፤ ያከብራል፡፡ እኛ በሥራችሁ ስኬት የምንመኘው ለቆማችሁለት የፖለቲካ ዓላማ ብቻ ሳይሆን ከህወሃት/ኢህአዴግ አገዛዝ ራሳቸውን ነጻ ለማውጣት አቅቷቸው መፈናፈኛ ላጡትም የመወሰን ኃይል እንደምትሰጧቸው በማመን ነው፡፡

አገራችን ካለችበት ወቅታዊ ሁኔታ አኳያ የበርካታዎች ጥያቄ “ህወሃት/ኢህአዴግን በምን ዓይነት የተሻለ አስተዳደር እንዴት መለወጥ ይቻላል የሚለው ነው?” ይህ ጥያቄ “እኛ ኢትዮጵያውያን የዘርና የጎሣ ትንንሽ አጥሮቻንን አፍርሰን ሁሉን አቀፍ ትግል ለማድረግ ተዘጋጅተናል ወይ?” ብለን ራሳችንን መልሰን አንድንጠይቅ የሚያደርገን ነው፡፡ እንዲሁም ከጎሣ ይልቅ ለሰብዓዊነት ቅድሚያ በመስጠትሁሉም ነጻ ሳይወጣ ራሳችንን ነጻ ለማውጣት እንችላለን ወይ? ብለንም እንድንጠይቅ የሚያስገድደን ነው፡፡

ህወሃት/ኢህአዴግ ከኢትዮጵያ አልፎ ለቀጣናው እንዲሁም ለመላው አፍሪካ “የሚተርፍ” እኩይ የዘርና የጎሣ ፖለቲካ በማስፋፋት አገራችንን እንደዚህ ባለ አሳሳቢ ደረጃ ላይ በጣለበት በአሁኑ ወቅት የብዙዎች ጭንቀት አገራችን ወደ ምን ዓይነት አዘቀት ውስጥ እየገባች ይሆን የሚለው ከሆነ ዓመታት ተቆጥረዋል፡፡ ነገር ግን ይህንን ፍርሃት ወደ ተስፋ የሚቀይር አማራጭ እስካሁን ተግባራዊ መሆን ባለመቻሉ አማራጭ የጠፋ ይመስል ህወሃት/ኢህአዴግም “እኔ ከሌለሁ …” እያለ ያስፈራራል፤ ተቃዋሚዎችም በእርስበርስ ሽኩቻ የህዝብ አመኔታ በማጣት ወደ አለመታመን ከመሄዳቸው የተነሳ መልሶ ተዓማኒነትን ለማግኘት ጥረት እያደረጉ ቢሆንም ገና ብዙ የሚቀር አለ፡፡ ይህም ሆኖ ግን ለኢትዮጵያ ሕጋዊ አማራጭ በመሆን ለሕዝባችን መፍትሔ የምታመጡበት ወሳኝ ጊዜ አሁን መሆኑን የጋራ ንቅናቄያችን ያምናል፡፡

እንደምታውቁት የዛሬ ዓመት ምርጫ የሚካሄድበት ጊዜ ነው፡፡ ምርጫውንና አመራረጡን ከሥሩ ጀምሮ የተቆጣጠረው ህወሃት/ኢህአዴግ ሆኖ ሳለ በኢትዮጵያ ውስጥ ነጻና ፍትሃዊ ምርጫ ይካሄዳል ብለን አናምንም፡፡ ሆኖም ከተቃዋሚ ፓርቲዎች በኩል የሚፈለገው ተግባር ከተከናወነ በአገራችን እውነተኛ ለውጥ ይመጣል ብለን እናምናለን፡፡ ዓመኔታ የሚጣልበት አማራጭ ከተገኘ ዓለምአቀፉ ኅብረተሰብ ህወሃት/ኢህአዴግን አንቅሮ ለመትፋት ከምንጊዜውም ይልቅ ዝግጁ ነው፡፡ ይህንንም የምንለው ከምንም ተነስተን ሳይሆን ድርጅታችን በአውሮጳ፣ በሰሜን አሜሪካ እና በሌሎች የዓለም ክፍሎች ባለው የግንኙነት መስመር ከሚያገኘው ተጨባጭና ተዓማኒ መረጃ በመነሳት ነው፡፡ በምዕራቡ ዓለም ዘንድ ህወሃት/ኢህአዴግ በኢትዮጵያ ውስጥ የሚያራምደው የዘር ፖለቲካ፣ የሚከተለው እጅግ ጭቋኝ ፖሊሲ፣ በየጊዜው በሚያወጣቸው አረመኔያዊ ህግጋት፣ ወዘተ ኢትዮጵያን ለከፍተኛ አደጋ የጣለና ለአህጉሩ መጥፎ ምሳሌ እየሆነ በመምጣቱ በኢትዮጵያ የሥርዓት ለውጥ የመከሰቱ ጉዳይ ከምንጊዜውም በላይ አሳማኝ የሆነበት ጊዜ ላይ ይገኛሉ፡፡ አሁንም ጥያቄው “ህወሃት/ኢህአዴግን ማን ይተካዋል?” የሚለው ነው፡፡ይህንን የመመለሱ ኃላፊነት በሁሉም ኢትዮጵያውያን ላይ የወደቀ ቢሆንም በተለይ አገር ውስጥ ያላችሁት የፖለቲካ ፓርቲዎች በቅድሚያ ልትመልሱት የሚገባ ጥያቄ ነው፡፡ አመኔታ የሚጣልበት አማራጭ ሆናችሁ የመቅረባችሁ ሁኔታ ስለምርጫው ነጻና ፍትሃዊነት ከመጠየቅ ባልተናነሰ መልኩ ተጠይቆ መልስ ሊሰጠው የሚገባ ነው፡፡

አገራችን ያለችበትን ወቅታዊ ሁኔታ ለእናንተ ማስረዳት የሚያስፈልግ አይመስለንም፡፡ በየቀኑ የሚፈጸመውን በደልና ግፍ መከታተል ብቻ ኢትዮጵያ ወዴት እየሄደች እንደሆነ በበቂ ሁኔታ የሚያመላክት ነው፡፡ ህወሃት/ኢህአዴግ እንደ ተቀጣጣይ (ክላስተር) ቦምብ በየቦታው የበተነው የጎሣ ፖለቲካ ፈንጂ ከፋፍሎ በመግዛት ለራሱ የሥልጣን ማቆያ ቢጠቀምበትም በአሁኑ ጊዜ አገራችንን ከላይና ከታች እያነደዳት ይገኛል፡፡ ከዚህ አኳያ በአገራችን ላይ ሊፈነዳ የሚችለው ነገር ሁሉንም የሚያሳስብ እንደሆነ በእርግጠኝነት መናገር ይቻላል፡፡ ህወሃት/ኢህአዴግ ራሱ በፈጠረው ችግርና በበተነው መርዝ ራሱን በራሱ ሊያጠፋው እንደሚችል ከድርጅቱ ውስጥ የሚታዩት የሥልጣን ሽኩቻዎች ሁሉም “ሳይቀድሙኝ ልቅደም” በሚል አስተሳሰብ እንደተወጠረ የሚያመለክት ነው፡፡ አገራችን ነጻነቷን ከመጎናጸፏ በፊት ይህንን ዓይነቱ የህወሃት/ኢህአዴግ እርስበርስ መበላላት የሚያሳስባቸው ኢትዮጵያውያን እጅግ በርካቶች ናቸው፡፡ ከሁሉ በላይ ደግሞ እናንተ ባላችሁ ኃላፊነት ይህንን በውል የምታጤኑት እንደሆነ የጋራ ንቅናቄያችን ያምናል፡፡

ህወሃት/ኢህአዴግ ከውስጥ በሚነሳበት ግፊትና የመበላላት ስጋት፤ ከውጪ በሚመጣበት ተጽዕኖ ወይም በሁለቱ ጥምረት ከሥልጣን መወገዱ የማይቀር ነው፡፡ ይህንን የሚቀበል ካልሆነም ሥርነቀል ተሃድሶ ማድረጉ እየጎመዘዘው የሚጠጣው ሐቅ ነው፡፡ በየትኛውም መልኩ የሚከሰተው ለውጥ አገራችንን መልሶ መልኩን ለቀየረ በዘር ላይ ለተመሠረተ አገዛዝ አሳልፎ የሚሰጣት መሆን የለበትም፡፡ ይልቁንም የሚመጣው ለውጥ ሕዝባችንን እውነተኛ ነጻነት የሚያጎናጽፍ፣ ፍትሕ የሚሰጥና ወደ ዕርቅ የሚመራ መሆን ይገባዋል፡፡ አገራችን በዚህ ጎዳና ላይ እንድትጓዝ የማድረጉ ኃላፊነት የእናንተ እንደሆነ የጋራ ንቅናቄያችን ያሳስባል፡፡

ይህ ደግሞ ሥልጣን ከመጨበጥ ባለፈ ምኞት ላይ የተመሠረተና እያንዳንዱ ነጠላ ፓርቲ ከሌሎች ጋር በኅብረት በመሥራት ተግባራዊ ሊያደርግ የሚገባው መሠረታዊ ዓላማ ነው፡፡ አገራችን ካለችበት ታላቅ ችግር አኳያ የፓርቲዎች መተባበርና ከተቻለም መዋሃድ ወደ መፍትሔ በሚወስደው መንገድ ላይ የመጀመሪያው ስኬት ነው፡፡ ይህ ግን በቀላሉ አይገኝም፤ ሆደ ሰፊ መሆንን፣ ከራስ ይልቅ ለአገርና ለሕዝብ እንዲሁም ለመጪው ትውልድ ማሰብን፣ ከሁሉ በላይ ደግሞ ከፍተኛ የመንፈስ ልዕልናን የሚጠይቅ ነው፡፡ ሥልጣንን፣ የራስን ክብር፣ የበላይነትን፣ “እኔ ከሌላው የተሻልኩ ነኝ” ማለትን፣ ወዘተ እያውጠነጠኑ ለአገር አስባለሁ ማለት በእጅጉ አስቸጋሪ ነው፡፡ “ከጠላት” የላቀ የመንፈስ ልዕልና ከሁሉም ይጠበቃል፡፡

በመጪው ምርጫ ከምንጊዜውም በበለጠ በመጽናት ለለውጥና ለነጻነታችን የምንታገልበት ሊሆን ይገባል፡፡ የኢትዮጵያ ሕዝብ የናፈቀውን ነጻነት ሊጎናጸፍ የሚችልበት አማራጭ ሊፈጠር እንደሚችል አኢጋን ያምናል፡፡ ይህ ሊከሰት የሚችለው በአገር ውስጥ ያላችሁት የፖለቲካ ፓርቲዎች ጥቃቅን ልዩነታችሁን አስወግዳችሁ አጀንዳችሁን ሕዝባዊ በማድረግ በኅብረት ለመሥራት ስትወስኑ ነው፡፡ የጋራ ንቅናቄያችን ባደረገው ጥናት አብዛኞቻችሁ ያላችሁ ልዩነት መሠረታዊ እንዳልሆነ ለመረዳት ችሏል፡፡ ይህም የሚያሳየው እርስበርስ ከሚያለያያችሁ ነገሮች ይልቅ ሊያስማሟችሁ የሚችሉት በርካታዎች እንደሆኑ ነው፡፡ በተለይ በአመራር ላይ ያላችሁ በተለያየ ጊዜ ከሌሎች ጋር የተከሰቱ ልዩነቶችና ግጭቶች እንዲሰፉ ምክንያት ከመሆን ይልቅ ለአገርና ሕዝብ በማሰብ ኢትዮጵያን የመታደግ ኃላፊነት ወድቆባችኋል፡፡ አገር ከሌለ ምንም ሊኖር አይችልም፤ እንደ ትልቅ የያዛችሁት ልዩነትና ችግርም ከንቱ ይሆናል፤ አብሮ ይከስማል፡፡

በተደጋጋሚ የሚሰማው ነጠላ ዜማ “በኢትዮጵያዊ ውስጥ ተስፋ የሚጣልበት ተቃዋሚ ፓርቲ የለም” የሚል ነው፡፡ በእርግጥ ለዚህ ጥያቄ ዋንኛ ተጠያቂው ኢህአዴግ ነው፡፡ ምክንያቱም በአስመሳይ ዲሞክራሲና ተግባራዊ ባልሆነ ሕገመንግሥት ሕዝባችንን ከመጠርነፍ አልፎ የፖለቲካ ፓርቲዎችንም በተመሳሳይ ሁኔታ ሸብቧቸዋል፡፡ ህወሃት/ኢህአዴግ የሚከተለው ፕሮግራም በኢትዮጵያ ውስጥ ጠንካራ የፖለቲካ ፓርቲ እንዳይኖር ያደረገ ለመሆኑ ማንም የሚክደው አይደለም፡፡ ሆኖም ግን በኢህአዴግ ብቻ እያመካኙ መኖር ተቀባይነት የሌለው አካሄድ ነው፡፡እያንዳንዱ የተቀናቃኝ ፖለቲካ ፓርቲ ዓላማው የኢህአዴግን መሰሪነትና አፋኝነት ለመስበክ ሳይሆን ሕዝብን ለነጻነት ማብቃት ነው፡፡ እታገለዋለሁ ከሚለው አካል መላቅ ካልቻለ ለትግል ብቁ ነው ለማለት ያስቸግራል፡፡

ሽንፈት ላይ እያተኮሩና የጠላትን ኃይለኛነት እየሰበኩ ድል አይገኝም፡፡ ልዩነትን እያራመዱ ኅብረትና አንድነት ተግባራዊ መሆን አይችልም፡፡ለአገራዊ ዕርቅ እንሰራለን እያሉ በፓርቲ መካከል ከዚያም በታች በግለሰብ ደረጃ መተራረቅ ካልተቻለ ብሔራዊ ዕርቅ ከቀን ቅዠት አያልፍም፡፡ እያንዳንዳችሁ የፖለቲካ ፓርቲዎች መድረክ፣ መኢአድ፣ አንድነት፣ ሰማያዊ፣ ኦህኮ፣ አረና፣ እና ሌሎች እጅግ በርካታ ፓርቲዎች የተቋቋማችሁትና ዓላማ ያደረጋችሁት ኢህአዴግን እየተቃወማችሁ ለመኖር እንዳልሆነ የፓርቲ ፕሮግራማችሁ ይመሰክራል፡፡ ወይም ዓላማችሁ የራሳችሁን የፓርቲ ምርጫ የማድረግና ፕሬዚዳንት (ሊቀመንበር)፣ ምክትል፣ ሥራ አስፈጻሚ፣ … በመምረጥ አዙሪት ውስጥ ራሳችሁን ላለማሽከርከር እንደሆነ ከማንም በላይ ራሳችሁ ታውቁታላችሁ፡፡ ከዚህ አንጻር በጥንቃቄና በብዙ ጥናት የተቀመጠው የፓርቲያችሁ ፕሮግራምና ዓላማ ለአገራችን አንዳች ለውጥ ሳያመጣ እንደዚሁ እንዳማረበት ቢቀመጥ ለሕዝብ የሚያመጣው ትርፍ ምንድርነው? እናንተንስ ለመቃወም ብቻ የምትሰሩ አያደርጋችሁምን? ለኢህአዴግና ወዳጆቹስ ጣት የሚጠቁሙበትን ዕድል እየሰጣችሁ እስከመቼ ትኖራላችሁ? ስለዚህ የእስካሁኑ በነጠላ የመጓዙ ጉዳይ ካልሰራ በኅብረት የመሥራቱ ጉዳይ የግድ ይሆናል፡፡ ይህ ወሳኝ ጉዳይ እንደሆነ አኢጋን ያምናል፡፡

የጋራ ንቅናቄያችን ከበርካታ ዓለምአቀፋዊ ድርጅቶችና ታዋቂ ግለሰቦች ጋር ካለው ግንኙነት አኳያ በኢትዮጵያ ጉዳይ ላይ መረጃ ይሰበስባል፡፡ በቅርቡ አንድ ታዋቂ የምዕራቡ ዓለም የፖሊሲ አውጪ ሲናገሩ “ኢትዮጵያውያን የምዕራቡ ዓለም ነጻ ያወጣናል ብለው በጭራሽ ማመን የለባቸውም፡፡ ከውጭ የሚላከውን ዕርዳታና ድጋፍ ብናቆም እንኳን ይህ የሚሆን አይደለም፡፡ የለውጥ አራማጅና መሪ መሆን ያለባቸው ኢትዮጵያውያን ራሳቸው ናቸው እንጂ ለጋሽ መንግሥታት አይደሉም፡፡ ኢትዮጵያውያን ይህንን ሊረዱ ይገባል፡፡ ኢትዮጵያውያን ራሳቸው ከህወሃት/ኢህአዴግ የተሻለ አማራጭ በሚፈጥሩበት ጊዜ እኛ የግድ እንድንደግፋቸው ያደርጉናል” በማለት ለጋራ ንቅናቄያችን ምስክርነታቸውን ሰጥተዋል፡፡

ይህ ንግግር በአገር ውስጥ ለምትገኙት ብቻ ሳይሆን በዳያስፖራ ለምንገኘውም ልንገነዘብ የሚገባው ሐቅ ነው፡፡ ነጻነት ከምዕራቡ ዓለም ብቻ ሳይሆን በዳያስፖራ ከሚገኙት ኢትዮጵያውያንም ሊመጣ አይችልም፡፡ የነጻነታችንን ጥያቄ ተግባራዊ የሚሆነው እናንተ በአገር ውስጥ የምትገኙ የፖለቲካ ፓርቲዎች በኅብረት በመሥራት ሕዝባችንን ለለውጥ ስታስተባብሩት ብቻ ነው፡፡ እኛ ይህንን ከራሳችን ትከሻ ላይ ለማውረድና እናንተን በኃላፊነት ለመጠየቅ የምንጭነው ሳይሆን አገር ውስጥና ውጭ መሆናችን በታሪክም ይሁን በሌላ ምክንያት የተከሰተ በመሆኑ በቅንነትና በሐቅ የምንናገረው እውነታ ነው፡፡ እኛም ከአገር ውጭ ነን በማለት እጃችንን አጣጥፈን የምንቀመጥ ሳይሆን በአገር ውስጥ የሚካሄደውን ትግል የመደገፍ፣ የማገዝ፣ የምዕራባውያንን አመለካከት የማስቀየር፣ በአገር ውስጥ የሚካሄደውን የሰብዓዊ መብት ረገጣ የማሳወቅ፣ … ኃላፊነት እንዳለብን በመገንዘብ ነው፡፡ አኢጋን ይህንን ዓይነቱን ተግባር ሲያካሂድ የቆየ አሁንም ከአገር ውስጥ የሚመጣውን ጥያቄ ለመመለስና በሚችለው ሁሉ ለማገዝ ሙሉ ዝግጁ መሆኑን ለመግለጽ ይወዳል፡፡

ከዚህ በፊት በተካሄዱት ምርጫዎች እንደታየውና በፓርቲያችሁ ፕሮግራም ላይ እንደሰፈረው እንደ ፖለቲካ ፓርቲ በምርጫ ተወዳድራችሁ ሥልጣን የመያዝ ዓላማ እንዳላችሁ ግልጽ ነው፡፡ ሆኖም ግን ማናችሁም ብትሆኑ በነጠላ ፓርቲነት ተወዳድራችሁ ሥልጣን በመያዝ ለውጥ እንደማታመጡ በግልጽ ልንነግራችሁ እንወዳለን፡፡ በምርጫ አሸነፋችሁ ቢባል እንኳን ሥልጣን የሌለው ቢሮ ከመያዝና የህወሃት/ኢህአዴግ አሻንጉሊት ከመሆን እንደማታመልጡ እሙን ነው፡፡ ይልቁንም ይህ ዓይነቱ አካሄድ ህወሃት/ኢህአዴግ በተለይም ለምዕራቡ ዓለም ለሚደሰኩረው የይስሙላ ዴሞክራሲ ማረጋገጫ ሆኖ በማቅረብ የኢህአዴግ ዕድሜ መቀጠያ መድሃኒት ነው የምትሆኑለት፡፡ ስለዚህ ከመጪው ምርጫ አኳያ ትግሉ የተናጠል ሳይሆን ፓርቲዎች በኅብረት በመሆን ኢህአዴግን በእርግጠኝነት ሊተኩ የሚችሉበት አማራጭ ሊሆን ይገባዋል፡፡

በበርካታ አገሮች እንደሚታየው እናንተም በኅብረት በመሆን ኃይላችሁን አስተባብራችሁ ለሕዝባችሁ ስትሉ እርስ በርስ መጠላለፍ፣ መነቋቆር፣ መካሰስ፣ ወዘተ አሁኑኑ ማቆም ይገባችኋል፡፡ በእስራኤል፣ ብሪታኒያ፣ ጀርመን፣ … በተለያዩ ጊዜያት እንደታየው ፓርቲዎች ጥምር መንግሥት በመመሥረት ሕዝባቸውን ታድገዋል፣ አገልግለዋል፡፡ በኢትዮጵያስ ይህ ሊሆን የማይቻልበት ምክንያት ምንድርነው? መልሱን መመለስ የሚገባችሁ እያንዳንዳችሁ የፓርቲ አመራሮች ናችሁ፡፡

ይህ ሳይሆን የሚቀር ከሆነ በቅርቡ የፖለቲካ ታሪካችን እንደታየው በዚህም ዘመን በተመሳሳይ መልኩ ይደገማል፡፡ በዘመነ አጼ ኃይለሥላሴ የተነሳው የህዝብ ብሶት ዳር ሳይደርስ ደርግ ለራሱ አስቀረው፡፡ በደርግ ዘመን መከራውንና ስቃዩን ያየው ሕዝብ ህወሃት/ኢህአዴግ “የሕዝብ ብሶት” የወለደኝ ነው ብሎ ሲመጣ የመከራው ዘመን ማብቂያው የደረሰ መስሎት ተስፋ አደረገ፡፡ “ብሶት” ወለደኝ ያለው ኢህአዴግ ኢትዮጵያን ታይቶ በማይታወቅ የዘር “ድንበር” ከፋፍሎ የሕዝባችንን ብሶት ለ23ዓመታት በየቀኑ እያበዛው ይገኛል፡፡ አሁንም ጥንቃቄ ወስዳችሁ ሁላችሁም ለሕዝባችን የሚሆን መፍትሔ የማታመጡ ከሆነ የሕዝባችን ብሶት እንዲቀጥል የምታደርጉ ብቻ ሳይሆን በመጪው ትውልድም ከመጠየቅ አታመልጡም፡፡

በቅንጅት ጊዜ ሕዝብ እጅግ ተስፋ አድርጎ ውጤት ሲጠብቅ ቅንጅቶች “መቀናጀት” አቅቷቸው ጫፍ ላይ ደርሶ የነበረው የሕዝባችን ድል ገደል ገባ፤ በራሱ ተቀናጅቶ የነበረው ሕዝብ የህወሃት/ኢህአዴግ የበቀል እርምጃ ሰለባ ሆነ፡፡ የጋራ ንቅናቄያችን ከበርካታ ወገኖች ጋር ባለው ግንኙነት አሁንም ተመሳሳይ ችግር ይፈጠራል እያሉ ስጋታቸውን የሚገልጹልን ቁጥራቸው በርካታ ነው፡፡ በአገራችን ላይ በርካታ ችግሮች የተጋፈጥን ቢሆንም ከፈጣሪ በኩል ግን ሁልጊዜ መፍትሔና የተበላሸውን የማስተካከል ዕድል አለ፡፡ ይህም ዕድል አሁን እንደሆነ አኢጋን ያምናል፡፡ ከዚህ አንጻር ጥቂት ሃሳቦችን ለማካፈል እንወዳለን፤

  1. በምንም መልኩ በኢትዮጵያ አማራጭ ፓርቲ የለም የሚለውን ተስፋ አስቆራጭ ንግግር አትቀበሉ፡፡
  2. ከሌሎች ፓርቲዎች ጋር አብራችሁ ልትሰሩ የሚያስችላችሁን ነጥቦች ዘርዝሮ በማውጣት በሚያስማማችሁ ጉዳዮች ላይ የጋራ አስተሳሰብ ልትወስዱ የምትችሉበትን መንገድ አመቻቹ፡፡
  3. በዕቅዳችሁና ከሌሎች ጋር በጥምረት በመሆን ምንም እንኳን አስቸጋሪ ቢሆን በዋንኛነት በአገራችን የፖለቲካ ምህዳር የሚሰፋበትንና ዕርቅ የሚመጣበትን መንገድ ከመቀየስ ተስፋ አትቁረጡ፡፡
  4. የፓርቲ ፕሮግራምና ማኒፌስቶ ከሰማይ የወረደ፣ የማይገሰስ፣ የማይሻርና የማይለወጥ የፈጣሪ ቃል አይደለም፡፡ ስለዚህ ወደ ውኅደት በሚደረገው ጉዞ መሻሻል፣ መለወጥ፣ መስተካከል፣ የሚገባው የፕሮግራም አንቀጽ የፓርቲያችሁን ኅልውና አደጋ ላይ እስካልጣለ ድረስ ተፈጻሚ ለማድረግ ሆደሰፊ ሁኑ፡፡
  5. ከመሪዎች ጀምሮ በፓርቲያችሁ ውስጥ ውህደትን፣ ጥምረትን፣ … ተግባራዊ ለማድረግና በጋራ ለመሥራት ዕንቅፋት የሚሆኑ ግለሰቦችን በግልጽ መውቀስና እንዲታረሙ ወዲያውኑ ማድረግ ወሳኝነት ያለው ተግባር ነው፡፡ “እገሌን እንዴት እወቅሰዋለሁ” ወይም “አቶ እገሌ የፓርቲያችን የጀርባ አጥንት ነው እንዴት ተሳስተሃል እላልሁ” በሚሉ የይሉኝታ አስተሳሰቦች ለአንድ ሰው ሲባል አገርና ሕዝብ መከራና ስቃይ እንዲቀጥል መደረግ የለበትም፡፡ አገር ለመምራት ፓርቲ መሥርታችሁ ሕዝብን በይሉኝታ መንግሥት ማስተዳደር ፈጽሞ አይቻልም፡፡ ለይሉኝታ በራችሁን ዝግ ይሁን፡፡
  6. ሁልጊዜ ለመምራት ሳይሆን ለመመራት ተዘጋጁ፡፡ የሰላማዊ ትግል መሪ መመሪያ ይኸው ነው፡፡ ለመመራት የተዘጋጀ መሪ ለመሆን ምንም አይቸግረውም፡፡ ከሥልጣንህም ተነሳ ሲባል ፓርቲውን አይገነጥልም ወይም “እኔ ከሞትኩ …” በሚል ጭፍን አስተሳሰብ በሕዝብ ላይ የውድመት ተግባር አይፈጽምም፡፡ ይህ ምንም የምንደባበቅበት ነገር አይደለም በተግባር ሲፈጸም የኖረ ነው፤ መስተካከልና መሻሻል የሚያስፈልገው ነው፡፡ ከመገልገል ይልቅ ለማገልገል ትሁት ሁኑ፡፡

የኢትዮጵያ ሕዝብ የሚፈልገው ትክክለኛ አስተዳደር ነው እንጂ ህወሃት/ኢህአዴግን በሌላ መተካት አይደለም፡፡ ሕዝባችን ይህ ያንሰዋል እንጂ አይበዛበትም፡፡ ስለሆነም “ኢህአዴግ ይነሳ እንጂ” የሚለው ጠባብና ሰንካላ ሃሳብ የእውነተኛ ለውጥ መርህ ስላልሆነ በጭራሽ ለሕዝባችን አትመኙለት፡፡ የኢትዮጵያ ሕዝብ ከእንግዲህ ወዲህ የሚያስፈልገው “ከጎሣና ዘረኝነት ይልቅ ሰብዓዊነት”የሚያብብባትና “አንዱ ብቻ ሳይሆን ሁሉም ነጻ የወጣባትን”፤ ፍትህ፣ ሰላምና ዕርቅ የሰፈነባትን አዲሲቷን ኢትዮጵያን ነው፡፡ ከዚህ ያነሰ ለውጥ በለውጥ ደረጃ ሊታሰብም ሆነ ሊታቀድ አይገባውም፡፡

እናንተ አገር ውስጥ ሆናችሁ በየጊዜው በምታደርጉት የመስዋዕትነት ተግባር የጋራ ንቅናቄያችን ከጎናችሁ ይቆማል፡፡ ሥራችሁንም በታላቅ አክብሮት ይከታተላል፡፡ የመስዋዕትነታችሁ ውጤት ፍሬ እንዲያፈራ የሚቻለውን ሁሉ ያደርጋል፡፡ በውጭ ከበርካታ ወገኖች ጋር ባለን ግንኙነት ለምትፈልጉን ሥራ በምንችለው ሁሉ ለመተባበር ፈቃደኛ መሆናችን እንገልጻለን፡፡ በተለይ በዕርቅ መንገድ ላይ ለአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ የሚጠየቀውን ሁሉ ለማድረግ ፈቃደኝነቱን ይገልጻል፡፡ ይህ ጉዳይ በዚህ ደብዳቤ ላይ ለፕሮቶኮል ብለን የምንናገረው እንዳልሆነ እንድትረዱልን እንፈልጋለን፡፡

አገራችን በበርካታ ድሎች ያንጸባረቀ ታሪክ ያላት ነች፡፡ ከሁሉ በበላይ የሚጠቀሰው የዓድዋ ድል በድጋሚ የሚፈጸምበት ጊዜ ቢኖር አሁን ነው፡፡ የዓድዋን የጦር ድል በፖለቲካው መድረክ እንድገመው፡፡ መጪውን ምርጫ ፖለቲካዊ የዓድዋ ድል የምንጎናጸፍበት እናድርገው፡፡ ነጻነታችን እንደ ዕርዳታ እህል ከምዕራባውያን የሚለገሰን አይደለም፡፡ ስለዚህ እኛው ራሳችን እንደ አድዋ ድል አንድ ሕዝብ ሆነን በመውጣት የራሳችን የምናደርገበት ጊዜ አሁን ነው፡፡ ቅንነት ካለ የጦር ሜዳውን አድዋ በፖለቲካው ሜዳ ላይ መድገም ይቻላል፡፡ አንድ ሊያደርጉንና ሊያስተባብሩን የሚችሉ “ምኒልኮችን” ለመጠቀም ፈቃደኛና ቅን እንሁን፡፡

እርስበርሳችን እንደ ወንድምና እህት ለመተያየትና ለመግባባት ፈጣሪ ቅን ልብ ይስጠን፡፡ እናንተንም ለፍትሕ፣ ለነጻነት፣ ለሰብዓዊነት፣ ለፍቅርና ዕርቅ ስትታገሉ ማስተዋልንና ጥበብን ይስጣችሁ፡፡

ከአክብሮት ጋር ለአገራችን ፈውስ እንዲመጣ የትግል አጋራችሁ፤

ኦባንግ ሜቶ
ዋና ዳይሬክተር፤
ለአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ (አኢጋን)

Email: obang@solidaritymovement.org
Website:www.solidaritymovement.org

በምስራቅ ጎጃም አርሶ አደሮች በፖለቲካ አመለካከታቸው የተነሳ ማዳበሪያ እየተከለከሉ ነው ተባለ

$
0
0

(ነገረ ኢትዮጵያ) በምስራቅ ጎጃም ዞን ጎንቻ ሲሶነሴ ወረዳ አርሶ አደሮች በፖለቲካ አመለካከታቸው ልዩነት ምክንያት ማዳበሪያና ምርጥ ዘር እየተከለከሉ መሆኑን የነገረ ኢትዮጵያ ምንጮች አስታወቁ፡፡ መንግስት ለአርሶ አደሮች በህብረት ስራ ማህበራት የግብርና ግብዓትና ግብይት በኩል የሚያቀርብ ሲሆን ይህም ማዳበሪያ የሚሸጠው የገበሬዎች ህብረት ስራ ማህበራት ላይ ነው፡፡ ሆኖም ሁሉም አርሶ አደሮች የማዳበሪያና የምርጥ ዘር አቅርቦት የማያገኙና ይህም ከአመለካከት ጋር በተያያዘ መሆኑን ምንጮች ጠቅሰዋል፡፡
news
አርሶ አደሮች ምርጥ ዘርና ማዳበሪያ እንዳያገኙ ከተደረጉባቸው ምክንያቶች የመጀመሪያ ተብሎ የተቀመጠው ለመለስ ዜናዊ ፋውንዴሽን መዋጮ ያላዋጡት ሲሆን፣ በ1997 ምርጫ ተቃዋሚ የነበሩ እንዲሁም ገዥው ፓርቲ በአርሶ አደሩ ላይ ባደራጃቸው 1ለ5 አደረጃጀት ጥናት መሰረት ‹‹ተቃዋሚ ናቸው›› የተባሉ አቅርቦቱን እንዳያገኙ ተደርጓል ተብሏል፡፡

በሌላ በኩል ህገ ወጥ የቤት ግንባታ በሚል የሚፈርሱ ቤቶች ከከተማ ወደ ገጠር እየተስፋፉ እንደሚገኙም ተገልጾአል፡፡ በአሁኑ ወቅት ከገጠር ወደ ከተማ እንዲገቡ የታቀዱና የገቡ እንዳሉና አርሶ አደሮች የይዞታ መብታቸውን ሳይነጠቁ መሬታቸውን እየተቀሙ እንደሆነ ተጠቆሟል፡፡
ለምሳሌ ያህልም በደብረ ማርቆስ አካባቢ የእርሻ መሬት ይዞታቸው እንደተጠበቀ ነገር ግን ወደ ከተማ የተከለሉ፣ ወደ ፊት ሊገቡ የተከለሉ መሆኑን ምንጮቻችን ጠቅሰዋል፡፡ በተመሳሳይ እናርጅናውጋ ውስጥ ወደ ከተማ እንዲገቡ ያልተወሰኑ የአርሶ አደሩ መሬቶች ላይ ቤት ሲገነባ ‹‹ህገ ወጥ›› እየተባለ ነው፡፡ በዚህም አርሶ አደሮቹ ለመሬታቸው ካሳ እየተከፈላቸው እንዳልሆነ ምንጮች ጨምረው አመልክተዋል፡፡

ህወሓት የቤተክርስያን ገንዘብ ዘረፈ

$
0
0

አብርሃ ደስታ ከመቀሌ

በትግራይ ምስራቃዊ ዞን ክልተ አውላዕሎ ወረዳ “አይናለም” የተባለ ጣብያ (ንኡስ ወረዳ) አለ። በዛ አከባቢ ያለው ደን “የመለስ ፓርክ” ተብሎ ተከልሏል። ኗሪዎቹ “የመለስ ፓርክ” መባሉ አልተዋጠላቸውም፤ ተቃውመውታል።
tplfለፈው ወር ነው። “ከመለስ ፓርክ” የተወሰነ ዛፍ ይቆረጣል። በዚህ ጉዳይ የተቆጡ ካድሬዎች የአይናለም ኗሪዎችን ሰብስበው ዛፉ የቆረጠው ማን እንደሆነ ይጠይቃሉ። አውጫጭ መሆኑ ነው። ህዝቡ ላለመናገር አደመ። ህዝቡ ስላልተናገረ ለስምንት ተከታታይ ቀናት ታሰረ፤ ቅጣት መሆኑ ነው። ህዝቡ የታሰረው ፖሊስ ጣብያ አልነበረም፤ ፖሊስ ጣብያ አይበቃውማ። በብዙ ሺ የሚቆጠር ህዝብ (ወጣቶች፣ አዛውንቶች፣ እናቶች በቃ ሁሉም) በረኻ ላይ በፖሊሶች ተከቦ ታስሮ ይውላል። ዝናብ ይደበደባል፤ ፀሓይ ይመታል። ህዝቡ ግን ይህን ሁሉ ስቃይ ችሎ በቃሉ ፀና። ካድሬዎቹ ከስምንት ቀናት በኋላ ተስፋ ቆርጠው ተውት። ህዝቡ ግን ተቀይሟል።

ከተወሰነ ግዜ በኋላ የማዳበርያ ጉዳይ መጣ። መዳበርያ ዉሰዱ ተባሉ። አንወስድም አሉ፤ በአንድ ቃል። ህዝቡ ያቀረበው ምክንያት መዳበርያ ለመግዛት ገንዘቡም ፍላጎቱም የለንም የሚል ነው። ካድሬዎች ህዝቡን ለማስፈራራት ሞከሩ፣ አሰሩ፣ አዋረዱ። አልተሳካላቸውም። የካድሬዎች የመጨረሻ ሓሳብ ህዝቡ ለማዳበርያ የሚሆን ገንዘብ ከሌለው ከቤተክርስያን ታቦት እንዲበደር ጠየቁት። ህዝቡ አሻፈረኝ አለ። ከታቦት ተበድረን ማዳበርያ አንገዛም፣ ከእግዚአብሄር ቤት ተበድረን ለመንግስት አንሰጥም አሉ።

ካድሬዎችም ማዳበርያው በተሽከርካሪ ጭነው ጣብያው (ቀበሌው) ላይ አራገፉት። ህዝቡም የምንከፍለው ገንዘብ የለንም አለ። ካድሬዎቹ ደግሞ የአይናለም ህዝብ ታቦት የሚገኝበት “መድሃኔዓለም ቤተክርስትያን” ጋ በመሄድ ለማዳበርያው ዋጋ የሚሆን ገንዘብ ይወስዳሉ። የታቦቱ ቄሶች ዝርፍያ ተፈፅሞብናል በሚል ተግባሩን ይቃወማሉ። ቄሶቹ አርፈው እንዲቀመጡ ይነገራቸዋል። አሁን ለማዳበርያው የሚሆን ገንዘብ በቤተክርስትያኑ ተወስዷል። ህዝቡም ተቃውሟል። አሁን የተቃውሞ ሰለማዊ ሰልፍ ለማድረግ እየሞከሩ ነው። ህወሓትም እያስፈራራቸው ነው። ቤተክርስትያን ተዘርፏል ብለው ተቃውሞ ያሰሙ ቄሶች ግን ታስረው ይገኛሉ።

እንዲህ ነው ዝርፍያ። ህወሓት የዝርፍያ ባህሏን እስካሁን ድረስ አጠናክራ ቀጥላለች ማለት ነው።

የወታደራዊ አገዛዝ 40ኛ ዓመት ከግንቦት 1966 –ግንቦት 2006 ዓ.ም

$
0
0

የሺዋስ አሠፋ
(ለነገረ ኢትዮጵያ ጋዜጣ እንደጻፉት)

የአንድ ሀገር ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ እንቅስቃሴዎች በሙሉ መንግስት ጨቋኝ ቁጥጥር ስር ሲሆኑ፣ የህዝቡ እንቅስቃሴዎችና ክንውኖች ከመንግስት በሚወርድ መመሪያ ብቻ ሲመክኑ፣ በህጋዊ ውሳኔና በፖለቲካዊ ውሳኔዎች መካከል ምንም ልዩነት ሲጠፋ ያች ሀገርና በውስጧ ያሉ ዜጎች በወታደራዊ አገዛዝ ስር የወደቁ ናቸው፡፡ በሀገሪቱ ያለው አገዛዝ በግልፅና በስውር በሚያሰማራቸው ወታደሮች፣ ፖሊሶች፣ ሚሊሻዎች፣ ደህንነቶች የነዋሪዎችን/የዜጎችን፣ የመንቀሳቀስ ሀሳብን የመግለፅና የመደራጀት መብት በቅርብ ክትትልና ቁጥጥር ስር ያለና የተገደበ ወይም ከፍተኛ ጫና ያለበት ይሆናል፡፡

mengistu hailemariam
የወታደራዊ አገዛዞች ሁሉም ለማለት በሚቻል መልኩ ወደ ስልጣን የሚወጡት በመደበኛ ጦርነት፣ በሽምቅ ውጊያ፣ በመፈንቅለ መንግስት ወይም በተለያዩ ሁኔታዎች በሚፈጠር የስልጣን ክፍተት ነው፡፡ በወታደራዊ አገዛዝ ካለፉ ሀገሮች መካከል ሶቪየት ህብረት፣ ምስራቅ ጀርመን፣ ደቡብ አፍሪካ፣ ቺሊ፣ ኩባ፣ ሰሜን ኮሪያ፣ ፓኪስታን፣ ኢትዮጵያ… ጥቂቶቹ ናቸው፡፡በሀገራችን እንዳየነውና ከሌሎችም ሀገሮች ተሞክሮ እንዳነበብነው የእነዚህ አገዛዞች ዋና ዋና ባህሪያት ከሚባሉት ውስጥ ከነሱ በፊት የነበሩ ስራዎችን መልካም ጅምሮችንም ጨምሮ መደምሰስና ማጥፋት፣ አዲስ መሰረትነው ለሚሉት ሀገርና ልማት ህዝቡን በእዝ ሰንሰለት በመጠርነፍ አስገድዶ ለማሰራት መሞከር፣ የሚከናወኑ ተግባራት በሙሉ በአስቸኳይ ጊዜና በዘመቻ ስራ እንዲሰሩ ማስገደድ፣ ስለተሰሩ ስራዎች ውጤት ሳይገመገም ሌላ ዘመቻ በማስከተል ህዝቡን ረፍት ማሳጣ፣ በሀገር ውስጥም ሆነ በውጭ ሀገር አንድ ኃይል በጠላትነት መሳልና የህዝቡን አይን ከአገዛዙ ድክመት ወደሚመጣው ጠላት ማዞር፣ በሚቆጣጠረው ብዙሃን መገናኛ የህዝቡን ሕይወት በፕሮፓጋዳ መያዝ፣ የተለየ ሀሳብ ያላቸውን ከጠላት ጋር በመፈረጅ፣ ሀገር ጠባቂና ለህዝብ ተቆርቋሪ መስሎ መታየት፣ የሀገሪቱን ሀብት በመበዝበዝ የገዥዎችን የአስተሳሰብ ድክመት በገፍ በሚወጣ የሀገር ሀብት ለማካካስ መሞከርና መሰል ድርጊቶች መለያዎቹ ናቸው፡፡

የዘውዳዊ ስርዓት እያረጀና ማስተዳደር እየተሳነው ሲሄድ ከወታደሩ የተሰባሰቡና ራሳቸውን ጊዜያዊ ወታደራዊ አስተዳደር ደርግ ብለው የሰየሙ፣ ከኢትዮጵያ መለዮ ለባሾች የተውጣጡ ለንጉሱ የማታለል ታማኝነትን እየገለፀ የቀዳማዊ ኃይለ ስላሴን መንግስት የገለበጠው ወታደራዊ ቡድን ስልጣኑን ያዘ፡፡
ሻ/ል ተስፋዬ ርስቴ ‹‹ምስክርነት›› በሚለው መፅሐፋቸው እንደገለፁት ደርግ የራሱ የሆነ ርዕዮት ዓለም አልነበረውም፤ ድንገት በተሰባሰቡ መኮንኖች የተሞላ ነበር፡፡ ከየካቲት 1966 ጀምሮ ከ6 ወራት ባነሰ ስልጣኑን በእጁ ካስገባ በኋላ ጊዜያዊ አስተዳደር መንግስት በመመስረት መለዮ ለባሾችን በሚኒስትርነትና በኮሚሽነርነት ማዕረግ በማስቀመጥ ከጠመንጃ አፈሙዝ ያገኘውን ስልጣን ለ17 ዓመታት ገፋበት፡፡

ከተለያዩ የጦር ካምፖች የተውጣጡ መኮንኖች አራተኛ ክፍለ ጦር ጠቅላይ መምሪያ ከተሰባሰቡ በኋላ በቅድሚያ መነጋገር የጀመሩት ምን እናደርግ? በሚል አጀንዳ ነበር፡፡ ይህ ግንቦት 1966 ምንም መርህ ያልነበረው ወታደራዊ ቡድን ከመስከረም 1967 ጀምሮ ስልጣኑን ጠቅልሎ በመያዝ ሀገሪቱን የጦርነትና የዘመቻ ቀጠና በማድረግ ሲያተራምሳት ኖረ፡፡ በዚህ ወቅት ከተደረጉትና ተመልካቹን ካስደነቁት ነገሮች አንዱ የአብዮቱ መሪና የደርጉ ሊ/መንበር የነበሩት ኮ/ል መንግስቱ ኃ/ማርያም ለጋዜጠኛ ሚሊዮን ተረፈ ሲመልሱ የሚሊቴሪ ልብሳቸውን በሱፍ ቀይረው እኔ ዋና ፀሐፊ ነኝ ‹‹ወታደራዊ መንግስት የታለ? አሁን ያለው መንግስት ሲቪል መንግስት ነው›› ሲሉ መደመጣቸው ነበር፡፡

ደርግ ሀገሪቱን ደቁሶ ከወደቀ በኋላ በእሱ እግር የተተካው ኢህአዴግ በሽግግር መንግስቱ ውስጥ ያካታተቻው ሚኒስትሮች ጋንታ መሪዎች፤ ተዋጊና አዋጊ ወታደሮች የነበሩ ሲሆኑ ከአቶ መለስ ዜናዊ ጀምሮ ሁሉም ባለስልጣናት የወታደር ልብሳቸውን ለውጠው ሙሉ ሱፍ የለበሱ ወታደሮች ናቸው፡፡ ስብሃት ነጋ፣ ስየ አብርሃ፣ ፀጋዬ በርሄ፣ አባይ ወልዱ፣ አዲሱ ለገሰ፣ በረከት ስምኦን፣ አባዱላ ገመዳ ወዘተ ሁሉም ወታደሮች የነበሩ ሲሆን አንዳንዶቹ ከጄነራልነት በቀጥታ አቶ ወደሚል ማዕረግ ወርደው አገዛዙን ሲቪል ለማስመሰል የተሞከረበት መንገድ ቢታይም እንደ 1997 ዓይነት ፈታኝ ጊዜ ሲመጣ ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ጀምሮ ሁሉም አዋጊ ጄነራሎች ሆነው ታይተዋል፡፡

በብዙኃን ሲቪል ህብረተሰብ እንደሚታወቀው ወታደር በከፍተኛ ታዛዥነትና ዲሲፕሊን የሚያምን፣ ቀድሞ በገባ የሲኒየሪቲ ባህል የሚገዛ (ይሄ ዛፍ ከአንተ ቀድሞ እዚህ ግቢ የበቀለ በመሆኑ የሲኒየር ሰላምታ ስጥ ሲባል እስከመቀበል የሚደርስ)፣ ለ6 ወራት ባገኘው ስልጠና ከ60 ዓመታት በላይ
የሚኖርበት፣ በበዓልም ሆነ በአዘቦት፣ በሰርግም ይሁን በለቅሶ በጠዋት ተነስቶ እንቅስቃሴ የሚሰራ፣ ፂሙንና ፀጉሩን የማስተካከል የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ካልሰራ፤ ጫማው ካልተቀባ፣ የሸሚዙ ኮሌታ ካልነፃ፣ ሱሪው ቀጥ ብሎ ካልተተኮሰ፣ ቁርሱን የማይቀምስ ህይወቱን በሙሉ በተጠንቀቅ የሚኖር፣ ለሀገሩ ጋሻና መከታ የሚሆን፣ ሀገሪቱ በአገዛዝ ስር ስትሆን ደግሞ የአለቃው ዱላ የሚሆን ነው ወታደር ማለት፡፡ ይህን የወታደር ህይወት በመንግስት ስርዓት ውስጥ ስናየው ዛሬ ሀገራችን ያለችበት አጠቃላይ ሁኔታ ያሳየናል፡፡ ለሚከናወኑ ማህበራዊም ሆነ ኢኮኖሚያዊ ተግባራት ህዝብን አማክሮና የህዝቡን ይሁንታ አግኝቶ ከመንቀሳቀስ ይልቅ በተለመደው ወታደራዊ አሰራር የአንድን ግለሰብ ሀሳብ ባለው የጥርነፋ መዋቅር መሰረት ከላይ ወደታች ለማውረድና ለማስረፅ ሌት ከቀን በሚዲያ መለፈፉና በየቀበሌው ከአመት አመት ስብሰባ የካድሬዎቹና የህዝቡ ህይወት ሆኖ እያየን ነው፡፡

ለ23 ዓመታት በዚህ ሁኔታ የሚገዙን ግለሰቦች ከስማቸው በፊት ያለውን ቅፅል ቢቀይሩም፣ ወታደራዊ መለዮአቸውን ቀይረው የሲቪል ልብስ ቢለብሱም ሲያዋጉና ሲያዋጉ የኖሩ ናቸው፡፡ ሀገራችን ኢትዮጵያም ለ17 ዓመታት በደርግ፣ ለ23 ዓመታት በኢህአዴግ በጠቅላላው ለ40 ዓመታት በወታደራዊ አገዛዝ ስር የምትማቅቅ ሀገር ናት፡፡የደርግ ባለስልጣናት የነበሩት መንግስቱ ኃ/ማርያም፣ አጥናፉ አባተ፣ ተፈሪ በንቲ፣ አማን አንዶም፣ መላኩ ተፈራ፣ ለገሰ አስፋው፣ ፍ/ስላሴ ወግደረስ እና ሌሎችም ይህንና ያንን ያደርግነው መጀመሪያ ኢህአፓ ስላደረገው ነው ወይም በመኢሶን ምክር ነው በማለት የአገዛዙን መጥፎ ድርጊቶች በሌላ ወገን ለማላከክ ቢሞክሩም የመንግስታቸውን ወታደራዊ አገዛዝነት አይከዱም፡፡
eprdf-tplf
የኢህአዴግ ባለስልጣናት ግን ፈፅሞ በወታደርነት ያልተሰለፉ ለማስመሰል ከሲቪል መካከል በምርጫ የመጡ ተደርገው እንዲታዩ ጥረት ሲያደርጉ ይስተዋላል፡፡ እውነታው ግን በወጣትነት ጊዜያቸው በተቀረፀባቸው የአድርግ አታድርግ በወታደራዊ ትዕዛዝ የተቀየዱ መሆናቸው ነው፡፡ ይህ የወታደር መስመራዊ
ትዕዛዝ በዘርና በወንዝ ልጅነት ሲጠፈር ፍፁም የሆነ የጋሪ ፈረስ አይነት መከተልን ያመጣል፡፡ የችግሩም ምንጭ ጥልቀት ይሄን የተቀየደ አሰራር ወደ ሲቪል ተቋማት ለማውረድና በዚሁ መሰረት የጉልበትም ሆነ የአእምሮ ስራዎችን አስገድዶ ለማሰራትና ሀገርን ለማስተዳደር ሲሞክር ነው፡፡ በ2002 ዓ.ም መጨረሻ አካባቢ የኢትዮጵያ ቴሌኮሚኒኬሽን ኮርፖሬሽን መስሪያ ቤትን አስተዳደር ለፈረንሳይ ኩባንያ እንሰጣለን የሚል ትዕዛዝ መጣ፡፡ በወቅቱ ይህን ለማስፈፀም ላይ ታች ሲሯሯጡ የነበሩት አቶ ደብረ ጽዮን የተባሉ የህወሓት ወታደር የነበሩ በኋላ ልብሳቸውን ቀይረው ሚኒስተር የተደረጉ ሰው ነበሩ፡፡
በወቅቱ እዚያው እሰራ ስለነበር ከተሰብሳቢዎች መካከል ነበርኩ፤ በስብሰባው መክፈቻ ላይ እኒህ ግለሰብ ያስተላለፉት ትዕዛዝና ያንን ትዕዛዝ ለማስተላለፍ የተጠቀሟቸው ቃላት ቀጥታ ከኢታማጀር ሹሙ የተቀበሉትን ወታደራዊ ትዕዛዝ ለሰራዊቱ የሚያስተላልፉ ጄኔራል ይመስሉ ነበር፡፡ ስለ ጭቆና፣ ስለ
ኪራይ ሰብሳቢነት፣ ስለሽብር፣ ስለመበታተን አደጋ ምንም የማይመለከተው ቦታ ላይ ተናገሩ፡፡ ስለቴሌ መፍረስና ስሙም አትዮ ቴሌኮም ወደሚል መቀየሩን፣ ሰራተኛ እንደማይቀነስ ወዘተ… ብዙ ተናገሩ፡፡ የእኛን ሀሳብ ግን አንዱንም ለማድመጥ ፈቃደኛ አልነበሩም፡፡ የመጡት ወታደራዊ ትዕዛዝ ማስተላለፍ ስለነበር፡፡ላለፉት 40 ዓመታት በባንክ፣ በቴሌ፣ በመብራት ኃይል፣ በአየር መንገድ፣ በህንፃ ኮንስትራክሽን፣ በመንገድ ትራንስፖርት ላይ በመሳሰሉት ተቋማት ወታደራዊ ትዕዛዝና የዘመቻ ስራ ትንፋሽ እስኪያጥራቸው ሲያዋልባቸው ኖሯል፡፡ የሚደንቀው ግን አስበውና አቅደው ሳይሰሩ ያለፈውን ተግባር ድክመ
ትም ሆነ በጥንካሬ መነሻ ሳያደርጉ ለማደግ መታሰቡ አልፎም አድገናል መባሉ ነው፡፡ በሰላም በምንገዛላቸው ጊዜ ይህን ቢያደርጉም ስልጣኑን የሚነቀንቅ ሁኔታ ሲከሰት ልብስና ማዕረግ ቀያይረው በቴሌቪዥን መስኮት ብቅ ማለት የነዚህ ወታደራዊ አገዛዝ መሪዎች ባህሪ ነው፡፡ በሀገራችን ኢትዮጵያም ሆነ
በሌሎች እንደ ኩባ፣ በርማ እና ደቡብ ሱዳን መሪዎች የቅርብ ጊዜ ትዝታዎቻችን ናቸው፡፡

የወታደራዊ አገዛዝን ከነፍሱ የሚጠሉት ጄን ሻርፕ አገዛዞች በጣም ብልጥና ውስብስብ ሆነዋል ይላሉ፡፡ ህዝቡን እርስ በርስ ከማጋጨት በተጨማሪ ከዲሞክራት መንግስታት ጋር ለመወዳጀት ይሞክራሉ፣ ህዝባቸውን በውሸት ምርጫ በማታለል ከሲቪሉ የተመረጡ ለመምሰል ይጥራሉ፡፡ ለዓለም አቀፍ ድርጅቶች የተሳሳተ መረጃ በመስጠት በመሬት ላይ ከሚታየው ውጭ የሆነ እድገት ያስመዘገቡ ይመስላሉ ወዘተ፡፡ ስለዚህም ህዝቡ በመጀመሪያ የወታደራዊ አገዛዙን አመጣጥ፣ አሁን የቆመባቸውን ምሰሶዎችና፣ ወደፊትም በስልጣን ለመቆየት የሚፈነቅላቸውን ድንጋዮች ማወቅና መደራጀት ተገቢ ነው፡፡
በወታደራዊ አገዛዝ ለ40 ዓመታት እንደተያዝን እየታወቀ አሁንም በዚያው መንገድ ካለንበት ለመውጣት ሲታሰብ እጅግ ያስደንቃል፡፡ ወታደር ስሪቱ አንድ ነው፡፡ መጀመሪያ መደምሰስ፣ ቀጥሎ ማረጋጋት፣ ቀጥሎ ጊዜያዊ መንግስት መመስረት ቀጥሎ… አለቀ፡፡ ወታደራዊ አገዛዝን ለመጨረሻ ጊዜ ማስወገድ የሚቻለው ህዝብ በቃኝ ሲል፣ በአንድ ድምፅ አልገዛምሲል ነው፡፡ ይህን ለማድረግ ህዝቡ ማወቅ አለበት፡፡ ህዝቡ እንዲውቅ ደግሞ የህዝቡን ቀልብ የሳበና ህዝቡ የሚሰማውና የሚከተለው የፖለቲካ ድርጅት አስፈላጊ ነው፡፡በሀገሪቱ ያለው የመጨረሻው ትልቅ ኃይል ህዝቡ ነው፡፡ የፖለቲካ ድርጅት ህዝቡ እንደሚሰማው እርግጠኛ ከሆነ በሰላማዊ መንገድ አገዛዙን ሊያንበረክከው ይችላል፡፡ የአገዛዙ የመጨረሻ ጉልበት ወታደሩ ነው፡፡ ወታደሩን ዱላ በማድረግ ህዝቡን ማስፈራራት፣ ማሰር፣ መግደል የመጨረሻ አማራጭ ይሆናል፡፡ የፖለቲካ ድርጅቱ እያንዳንዱ ተራ ወታደር ከህዝቡ የወጣ እንዲሆነ በመገንዘብ ለእያንዳንዱ በተለያዩ ቦታ ለተሰማራው ወታደር ቅርብ እንደሆነ በመገንዘብ እያንዳንዱ በተለያዩ ቦታ ለተሰማራው ወታደር የቅርብ ዘመዴ ወይም ቤተሰቤ ከሚለውና መልዕክት/ደብዳቤ እንዲደርሰው ያደርጋል፡፡

በዚህ አይነት አንድ ወታደር ቢያንስ ከአምስት ሰዎች ከእኛ ጋር ቁም፤ ከወገንህ ጎን ቁም፤ የአምባገነን ዱላ አትሁን፣ ለሀገርህ እንጂ ለአገዛዙ አሽከር አትሁን የሚል ደብዳቤ ያደርሰዋል፤ የእነዚህን አይነት የሰላማዊ ትግል ስልቶች የህዝቡን የሞራል ልዕልና ከማሳደጋቸውም በተጨማሪ ለወታደራዊ አገዛዙ ፍፁም በማያዳግም ሁኔታ ሽባ የሚያደርጉና በአጭር ጊዜ ነፃነትን የሚያጎናፅፉ ናቸው፡፡ በሀገራችን የሰላማዊ ትግል ብዙ ያልተለመደና በህዝቡ ልብ ያልነበረ በመሆኑ ለ40 ዓመታት የተጫነብንን የብረት አገዛዝ ለመገርሰስ ሌላ ብረት በማንሳት መሞከር ወደሌላ አዙሪት እንደሚከተንም አብሮ መታሰብ ያለበት ሀቅ ነው፡፡ ሰላማዊና ህዝባዊ እንቢተኝነቱ የተሳካና ዴሞክራሲያዊ ስርዓት እንዲያመጣ የፖለቲካ ድርጅትና የብዙኃን መገናኛዎች ወሳኝ ሚና አላቸው፡፡ ጋሽ መስፍን (ፕ/ር መስፍን) እንደገለፁት የፖለቲካ ድርጅት ያስባል፣ ያቅዳል፣ ይወስናል፣ የብዙኃን መገናኛዎች ውሳኔውን ያስተላልፋሉ/ያሰራጫሉ፤ የትግሉ ዋና ኃይል የሆነው ህዝቡ ይፈፅማል/ይተገብራል፡፡ በዚህ አይነት የምንተገብራቸው፣ የ40 ዓመታት የጭቆና ቀንበር አሽንቀጥረን ለመጣል የሚያስችሉን 200 የሚደርሱ ዓለም አቀፍ ተቀባይነት ያላቸው የሰላማዊ ትግል ስልቶች መኖራቸውንም ልብ ይሏል፡፡

ቸር ይግጠመን!


የቀድሞው የጋምቤላ ርእሰ መስተዳድር ኦኬሎ ኦኳይ በሽብር ወንጀል ተከሰሱ

$
0
0

የቀድሞው የጋምቤላ ክልል ርእሰ መስተዳድር የነበሩት ኦኬሎ ኦኳይ በሽብር ወንጀል ክስ ተመሰረተባቸው።
news
ተከሳሾቹ የቀድሞው የጋምቤላ ክልል ርእሰ መስተዳድር የነበሩት ኢኬሎ ኦኳይ ፣ ዴቪድ ኡጁሉ፣ ኡቻን ኦፔይ ፣ ኡማን ኝክየው ፣ ኡጁሉ ቻም ፣ አታካ ኡዋር እና ኡባንግ ኡመድ ናቸው።

የፌደራል አቃቤ ህግ ሁሉንም ግለሰቦች ራሱን የጋምቤላ ህዝቦች ነጻነት ንቅናቄ /ጋህነን/ እና እህት ድርጅት ነው በሚሉት የጋምቤላ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ /ጋህነን/ በተሰኙ የሽብር ቡድን ድርጅቶች ከአመራር ሰጪነት እስከ አባልነት ተሳትፎ አላቸው በሚል ነው በሽብር ወንጀል ክስ የመሰረተባቸው።

1ኛው ተከሳሽ ኦኬሎ ኦኳይ በ1996 ዓ.ም የጋምቤላ ርእሰ መስተዳድር ነበሩ።

ክሱ በወቅቱ በክልሉ የሚገኙ የአኙዋክና የኑዌር ብሄረሰብ አባላት መካከል ግጭት ይቀሰቀሳል፣ በግጭቱም ከ 400 በላይ ሰዎች ህይወታቸውን አጥተዋል ፤ እኚህው ርእሰ መስተዳደሩ ሃላፊነታቸውን ተጠቅመው ግጭቱ በቁጥጥር ስር ሊያውሉ ሲገባ እንዳባባሱት ይጠቅሳል።

በዚህ ብቻ አላበቁም ግጭቱን አስመልክቶ ለተለያዩ የውጭ ሃገር መገናኛ ብዙሃን የተዛባ መግለጫ መስጠታቸውና የሚሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ እልቂቱን አባብሶት እንደነበርም ተጠቅሷል።

ኋላም ድርጊታቸው እንደሚያስጠይቃቸው በመረዳት የግል አጃቢያቸውና ሾፌራቸውን እንደያዙ ጥር 1996 ሃገር ከድተው መውጣታቸውን ፣ ሃገር ቤት ሆነው እልቂቱን ያባባሰ መግለጫቸውን መቀመጫቸውን ውጭ ሃገር ላደረጉ መገናኛ ብዙሃን መስጠት መቀጠላቸውን ክሱ አመልክቷል።

ወደ ኖርዌይም በማቅናት ጥገኝነት ካገኙና ሃገር ከድተው ከወጡ ከሶስት አመታት በኋላ ራሱን የጋምቤላ ህዝቦች ነጻነት ንቅናቄ/ጋህነን/ የተባለውን የሽብር ቡድን ለመቀላቀል በመወሰን በወቅቱ የዚህ ሽብር ቡድን መስራችና ሊቀመንበር ከሆነው ፒተር ካጋ ጋር በመገናኘት የውጭ ግንኙነት ሃላፊ በመሆን ተሹመው የሽብር ቡድኑን ተልእኮ ማስፈጸም አንድ ብለው መጀመራቸውን ክሱ አትቷል።

በአውሮፓና በአሜሪካ እየተዘዋወሩ የሽብር ቡድኑን አባላት በመመልመል ፣ ከአባላቱ በወር እስከ 50 ዶላር ሰብስበዋል የሚለው በክሱ የተጠቀሰ ሌላ ጭብጥ ሲሆን ፥ ታህሳስ 2000 ዓ.ም ላይ ከድርጅቱ የሽብር አመራሮች ጋር ያደረጉት ቴሌ ኮንፈርንስም በክሱ ላይ ተጠቅሷል።

በዚሁ ዓመት ጥር ወር ላይ ጋህነን ለሁለት ሲከፈል ኦኬሎ ኦኳይ አንዱን ክንፍ መስራቹ ፒተር ካጋ ደግሞ ሁለተኛውን መያዛቸው በክሱ ተመልክቷል።

የሊቀመንበርነትን በትረ ስልጣን እንደጨበጡ ኤርትራ በመሄድ በሽብር እቅዳቸው ላይ ለ45 ቀናት ያህል ውይይት አደረጉ፤ጀርመን ሳውዲ አረቢያ እና ስዊድን በመሳሰሉ ሃገራትም በማቅናት የሽብር ቡድኑን ለማጠናከር መከሩ ይላል ክሱ።

አሜርካም ተጉዘው በወቅቱ ከጋምቤላ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ /ጋዴን/ ሊቀመንበር ጆንሰን ኡጁሉ የሊቀመንበርነቱን ሃላፊነት ተረክበው ጋህነን እና ጋዴንን መርተዋል የሚለውም ተጠቅሷል።

በዚህ ሃላፊነታቸው ኡጋንዳ መጡ 860 አዳዲስ አባላትን መልምለው ወታደራዊና ፖለቲካዊ ስልጠና እንዲያገኙ ካደረጉ በኋላ ፤ አባላቱ ከደቡብ ሱዳን አማጽያን ጋር እንዲቀላቀሉ ማስደረጋቸውም ተዘርዝሯል።

ሁለተኛው ተከሳሽ ዴቪድ ኡጁሉ የደቡብ ሱዳን ዜግነት ያለው የ36 አመት ጐልማሳ ሲሆን ፥ በሽብር ቡድኑ የደቡብ ሱዳን ሃላፊ ነው።

ከመስከረም 2005 ዓ.ም ጀምሮ ባሉት ጊዜያት አሜሪካ ሃገር ሚኒሶታ ከተማ ለሽብር ስራው ማከናወኛ በተለያዩ ባንኮች የሚላክለትን ገንዘብ ሲቀበል ቆይቷል ፣ የመለመላቸው አባላቱ የደቡብ ሱዳን አማጺያንን እንዲቀላቀሉ አስተባብሯል የሚለው በክሱ ላይ ተጠቅሷል።

ከእርሱ ሌላ ኦኬሎ ኢኳይን ጨምሮ ሰባቱም ተከሳሾች ከሌሎች ተመሳሳይ የሽብር ድርጅቶች ያገኟቸውን ልዩ ልዩ የሽብር ስልጠና ተጠቅመው ፥ አንድ አስከፊ ድርጊት ሊፈጽሙ ዝጅግት በማድረግ ላይ እያሉ ነው በደቡብ ሱዳን የጸጥታ ሃይሎች የተያዙት።

በጋምቤላ ክልል ወርቅ በሚቆፈርባቸው የዲማ እና ጆር የተሰኙ ወረዳዎች ላይ በማቅናት ፤ በወርቅ ቁፋሮ ላይ የተሰማሩ በርካታ ወጣቶችን በማፈን የደቡብ ሱዳን አማጺ መሪ ዴቭድ ያውያው ስልጠና በሚሰጥበት ቦታ በማምጣት፣ ሰልጥነው የሽብር ቡድኑን እንዲቀላቀሉ የማድረግ አላማ እንደነበራቸው በክሱ ላይ ተመልክቷል።።

ይህንን ምክራቸውን ጠንስሰው ወደ ኢትዮዽያ መጥተው ተግባራዊ ለማድረግ ሲዘጋጁ ድንገት የኢትዮዽያ መንግስት ከደቡብ ሱIዳን ጋር ባለው የጋራ የጸጥታ ስራ ቅንጅት በቁጥጥር ስር ውለዋል ፤ ዛሬ በፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤተ 4ኛ የወንጀል ችሎት ቀርበውም ክሱ ተነቦላቸዋል።

የአማርኛ ቋንቋ ለማይናገሩት በአስተርጓሚ እንዲረዱት የተደረገ ሲሆን ፥ መንግስት ጠበቃ ያቁምልን በማለታቸውም ችሎቱን አቤቱታቸውን ተቀብሏል።

የተጠቀሰባቸው የህግ አንቀጽ ዋስትና የሚከለክል በመሆኑ ፥ ከሚመደብላቸወ ጠበቀ ጋር ተመካክረው የክስ መቃወሚያ እንዲያቀርቡ ችሎቱ ሰኔ 24 2006ን ተለዋጭ ቀጠሮ ይዟል።

በጥላሁን ካሳ

ምንጭ፦መንግስታዊ ራዲዮ ፋና

የመሬት ወረራን በመቃወሜ የተፈፀመብኝ በደል –አበበ ሆንጃ (ከሰበታ)

$
0
0

ነዋሪነቴ በሰበታ ከተማ አስተዳደር ወለቴ 03 ቀበሌ ጎጥ አራት ነው፡፡ የጎጥ ሰብሳቢ ሆኜ ለሁለት ዓመት ሰርቻለሁ፡፡ የቀበሌው የምክር ቤት አባል እና የኦህዴድ ኢህአዴግ አባል ሆኜ አገልግያለሁ፡፡ ድርጅታዊ እና ማንኛውንም ከላይ የሚወርደውን የመንግሥት መመሪያና ደንብ በህገ መንግሥቱ መሰረት
እንደ ዝቅተኛ አመራር ከድጋፍ ሰጪ አመራሮች በሚሰጠኝ መመሪያ እና ደንብ መሠረት በመፈጸም እና በማስፈፀም ሰርቻለሁ፡፡ የህዝብን ጥቅም ለማስከበር ለአካባቢ ፀጥታ፣ ልማት እና የህዝብን አደረጃጀት በቀበሌው ውስጥ ከየትኛውም የጎጥ አመራሮች በበለጠ ስሰራ ቆይቻለሁ፡፡ በ23/07/06 ዓ.ም ለቀበሌው የፀጥታ ዘርፍ በጎጡ ውስጥ ባለው ከፍታ ቦታም መሬት እየተወረረ ነው በማለት ሪፖርት ባደርግም የሚሰማኝ አላገኘሁም፡፡ የሚሰማኝ በማጣቴ መሬት እየወረሩ የነበሩትን ‹‹እየተሰራ ያለውን አቁሙ!›› ስላቸው ‹‹አንተ ምንድነህ? ከአንተ የበላይ የሚገኙት ባለስልጣናት ናቸው ያዘዙን!›› በማለት ስራቸውን ቀጠሉበት፡፡
addis-ababa-realethiopia-141
በማግስቱ ዓርብ ቀን 25/07/06 ዓ.ም ጧት 2፡00 ሰዓት አካባቢ ለቀበሌ 03 ሊቀመንበር ደውዬ ስለሁኔታው አስታውቄያለሁ፡፡ ሊቀመንበሩም ለደንብ አስከባሪዎች ደውሉላቸው በማለት መልስ ሰጥተውናል፡፡ ይህም በእንዲህ እንዳለ አንድ ምንም የሥራ ዓይነት የሌለው ደላላና የግንባታ ፈቃድ ሌላቸው የመንግስትና የህዝብ ሀብት የሆነውን መሬት በመቸብቸብ ሀብት ያካበተ ግለሰብ ረቡዕ ማታ የደንብ አስከባሪዎች እየጠራ ገንዘብ ሲያፍስ እንደዋለ በዓይኔ አይቻለሁ፡፡ ይህ በሆነበት ማግሥት እርስ በእርሳቸው ጀርባ በመግጠም አራቱ ቤቶች ወደ ሰሜን፣ አራቱ ቶች ደግሞ ወደ ደቡብ፣ አራቱ ተዋቅረው አልቀው ቆርቆሮ ሊመቱ ሲል፣ አራቱ ደግሞ ገና ጉድጓድ ተቆፍረው እያሉ ተደረሰባቸው፡፡ ዓርብ ቀን በ25/07/06 ዓ.ም ከሰበታ ከተማ አስተዳደር የቀበሌያችን ደጋፊ ሰው አመራር የሆነውን ግለሰብ ደውዬ በግምቱ 5፡00 ሰዓት አካባቢ በህገ ወጥ መንገድ የተሰሩት ቤቶች አስፈርሻለሁ፡፡

ይህንን የመንግስትና የህዝብ ሀብት የሆነውን መሬት ከመሬት ወራሪዎች እጅ አስፈርሼ ስላስመለጥኩ የጥቅሙ ተካፋይ የቦታዎቹ ባለቤትነት ማረጋገጫ ካርታ እና ምንም ዓይነት የግንባታ ፈቃድ የሌላቸው ግለሰቦችና ባለስልጣናት ሥልጣናቸወን ተጠቅመው በደል አድርሰውብኛል፡፡ የመሬት ወረራ ያደረጉ ግለሰቦች በእኔ ላይ ተደራጅተው በደል እያደረሱብኝ ይገኛሉ፡፡ ዐቃቤ ሕግ፣ ፖሊስ እና አስተዳደር እና ፀጥታ ከፍተኛ አድማ፣ ተፅዕኖ፣ ማዕቀብ እና በኑሮዬ ላይ ችግር በመፍጠር ከቤቴ እንድወጣ አድርገውኛል፡፡ አሁን ተባባሪ ሆኛለሁ፡፡ ህገ ወጥ ቤትን በማስፈረሴና የመሬት መቀራመቱን ለማስቆም በጣርኩ በ8/8/06 ዓ.ም ስምንት ኦሮሚያ ልዩ ኃይል አባላት እንዲሁም 11 አባላት የያዘ የከተማዋ ፖሊሶችን በመያዝ እንዲሁም 10 የሚደርሱትን የቀበሌ 03 ደንብ አስከባሪዎችን ግደሉት ተብለው መኖሪያ ቤቴን ከበው ውለዋል፡፡ እነዚህ አካላት የታዘዙት ከከተማው የፖሊስ አዛዥ ሲሆን በእኔ ላይ የሚወሰደው እርምጃ ምክንያታዊ ባለመሆኑ ‹‹ለምን እንገድለዋለን?›› ብለው ከአዛዡ ጋር የተከራከሩ የፖሊስ አባላት እንዳሉም ሰምቻለሁ፡፡ ባለቤቴ ‹‹ባልሽን አምጭ!›› ተብላ ያለአግባብ የዋስትና መብትዋን በመንፈግ ያለምንም የፍርድ ቤት ትዕዛዝ ታስራ ትገኛለች፡፡ ‹‹የመንግስት ያለህ›› በማለት ለህዝብ እና ለሀገር ታማኝ ሆኜ መሥራቴ፣ ከኪራይ ሰብሳቢዎች ጋር ለመተባበር ህገ-ወጥ ግንባታዎችን ማስፈረስ፣ አጥፉት፣ ግደሉት ያስብላል ወይ?

የአስተዳደር ፀጥታ ኃይሉ በሙሉ በእኔ ላይ ከፍተኛ አድማ፣ ተፅዕኖ፣ በመፍጠር ሊያጠፉኝ ተነስተዋል፡፡ ዛሬ ባለቤቴ ከመንግሥት ስራ ተፈናቅላ፣ እኔም እንዳይገሉኝ ሸሽቼ እገኛለሁ፡፡ ለአቅመ አዳም ያልደረሱ አራት ልጆች ያሉኝ ሲሆን ሁለቱ ልጆቼ የወለድኳቸውና ሌሎች ወላጅ አልባዎች በመሆናቸው የማሳድጋቸው ልጆቼ ዛሬ ለጎዳና አዳሪነት ሊዳረጉ ስለሆነ ለሚመለከተው ሁሉ ከጎኔ እንዲሰለፉ የድረሱልኝ ጥሪዬን አቀርባለሁኝ፡፡

በግንደ በረት በተማሪዎች እና በክልሉ ፖሊስ መካከል ከፍተኛ የሆነ ግጭት ተከሰተ

$
0
0

በምእራብ ሸዋ ዞን በኦሮሚያ ክልል በግንደበረት ወረዳ በተማሪዎች እና በወያኔ የፖሊስ ሃይሎች መካከል በተከሰተ ግጭት አንድ ተማሪ ሞቶ አራት መቁሰላቸውን የአከባቢው ምንጮች ገልጸዋል።
federal police
ከትላንትና ጀምሮ ሲንከባለል የመጣው ግጭት ከዚህ ቀደም በኦሮምያ ክልል ውስጥ ከተነሱ የተማሪዎች አመጽ ጋር ተያያዥነት ያለው እና ጥያቂውም የአዲስ አበባ ማስተር ፕላን እና የሞቱ የኦሮሞ ተማሪዎች ጋር የተያያዘ ሲሆን ዛሬ በቀጠለው ተቃውሞ ወደ 10 ሺህ የሚጠጉ ተማሪዎች እና የወረዳው ነዋሪ በጋራ ሰልፍ በመውጣት ቁጣቸውን የገለጹ ሲሆን አስተዳደሩ ድረስ በመሄድ ድምጻቸውን ሲያሰሙ የፌዴራል ፖሊስ በመምጣት የበተናቸው ቢሆንም ቀኑን ሙሉ በከተማው ከባድ ረብሻ እንደነበር እና ከቆሰሉ ተማሪዎቹም አንዱ መሞቱን የወረዳው ነዋሪዎች ተናግረዋል ሲሉ ምንጮቹ ጠቁመዋል።

በነገው እለት የ12ኛ ክፍል መሰናዶ ፈትና ከወሰደ በኋላ የተገደለውን ተማሪ ለመቅበር ይወጣል የተባለው ሕዝብ ተቃውሞ እንዳያሰማ የወረዳው እና የከተማው ባለስልጣናት በመስጋት ፖሊሶች ያሰፈሩ ሲሆን ሕዝቡ ቁጣው እንዳልበረደ እና በስፋት ተቃውሞው እንደሚቀጥሉ ነዋሪዎቹ ተናግረዋል።

በሪያድ የኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ ኮሚኒቲ ት/ቤት በገንዘብ እጥረት 3000 ህጻናትን በትኖ ሊዘጋ ነው * ወላጆች ለልጆቻቸው መበተን ዲፕሎማቱን ተጠያቂ ያደርጋሉ

$
0
0

Ethiopian Hagere ጀዳ በዋዲ

በስደት ዓለም የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ህጻናት በተመጣጣኝ ዋጋ ተቀብሎ በማስተማር ከፍተኛ አስተዋጾ እያበረከተ የሚገኘው በሪያድ አለም አቀፍ የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ ት/ቤት ላለትፉት ሁለት አስርት አመታት ሪያድ ከተማ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን የሚመኩበት እና የሚኮሩበት ተቋም ሆኖ መቆየቱ ይታወቃል። ከቅርብ ግዜ ወዲህ በወላጆች እና በሪያድ የኢትዮጵያ ኤምባሲ ዲፕሎማቶች መሃከል በተፈጠረው አለመግባባት ት/ቤቱ እንደተቛም ህልውናውን ጠብቆ ወደፊት መቀጠል እንደተሳነው የሚናገሩ ምንጮች ። ሰሞኑን የት/ቤቱ የኪራይ ዘመን እና የት/ቤቱ ህጋዊ ፈቃድ የግዜ ገደብ በመጠናቀቁን ተከትሎ በተቋሙ ህልውና ላይ የጋረጠው አደጋ አሳስቢ መሆኑን በመጥቀስ ከወራት በፊት በማን አለብኝነት ት/ቤቱን በበላይነት ተቆጣጥረው እንዳሻቸው ሲዘውሩት የከረሙት በሪያድ የኢትዮጵያ ኤምባሲ ሹማምንቶች በትምህርት ቤቱ ዙሪያ ተከሰቱ የተባሉትን የተወሳሰቡ ችገሮች ደረጃ በደረጃ መቅረፍ ተስኗቸው እራስቸውን ከተጠያቂነት ለማዳን የፌታችን አርብ ጁን 13 2014 አስቸኳይ የወላጆች ስብሰባ መጥራታቸውን ይገልጻሉ።

Saudi Arabia ethiopian school

በአምባሳደር መሃመድ ሃሰን አቀነባሪነት በዲያስፖራው ሃላፊ አቶ ተመስገን ኡመር አስፈጻሚነት ወላጆች በት/ቤቱ ጉዳይ አንድነት እንዳይፈጥሩ በብሄር ከፋፍለው በማጋጨት ዲፕሎማቱ ስልጣናቸውን መከታ በማድረግ በሾማቸው የቦርድ አባላት ያለምንም ኦዴት የት/ቤቱ ገቢ እና ወጪው ሳይታወቅ በሚልዮን የሚቆጠር ገንዘብ « ሪያል» ዘረፋ እንደተፈፀመበት የሚናገሩ እንዚህ ምንጮች ዛሬ ት/ቤቱ አመታዊ ኪራይ መክፈል ተስኖት ጉዳዩን ወደ ወላጆች ማምጣት እራስን ከተጠያቂነት ለማዳን ከሚደረግ እሩጫ ተለይቶ የማይታይ መሆኑንን ይናገራሉ። 3000 የሚሆኑ የስደተኛውን ማህበረሰብ ልጆች እንደሚያስተናገድ የሚነገርለት ይህ ት/ቤት ከእያንዳንዱ ተማሪ በወር እስከ 3 መቶ ሪያል በነፍስ ወከፍ እንደሚሰበስብ የሚገልጹት ውስጥ አዋቂዎች የት/ቤቱ ወረሃዊው ገቢ ብቻ ት/ቤቱ የራሱ የሆነ ህንጻ በማስገንባት ከኪራይ ነጻ መሆን ያስችለው እንደነበር አስታውሰው ከባለቤቱ በላይ አዋቂ ሆነው ት/ቤቱን በሞግዜትነት በሃይል ሲያስተዳደሩ የከረሙት እነዚህ ዲፕሎማቶች የት/ቤቱ ወላጆች እና የአካባቢው ማህበረሰብ በአንድ ወቅት ት/ቤቱን ከኪራይ ጥገኝነት ለመላቀቅ የራሴ ነው ብለው የሚመኩበትን ት/ቤት ለማስገንባት እንቅስቃሴ ላይ እያሉ በአምባሳደር መሃመድ ሃስነ ተዕዛዝ መታገዳቸውን ይናገራሉ ። ይህ በዚህ እንዳለ ለዚህ ተግባር የሚውል ከወላጆች ከአካባቢው ማህበረሰብ ለመሰብሰብ ታቅዶ ከነበረው 10 ሚልዮን ሪያል « በአሁኑ የኢትዮጵያ ምንዛሪ ከ50 ሚልዮን የሚበልጥ ብር » ውስጥ ግማሽ ያህሉ መሰብሰቡን የሚያስታውሱ ወላጆች ለገዘቡ ደህነት ሲባል በወቅቱ በአምባስደር መሃመድ ሃሰን ስም ከ 3 አመት በፌት አንድ ሳአውዲ አረቢያ የሚገኝ ባንክ ቤት ገቢ መሆኑን ይገልጻሉ። ዛሬ ት/ቤቱ እንደዚህ አይነት የተወሳሰቡ ችገሮች ውስጥ ባለበት ወቅት አመታዊ የኪራይ ገንዘብ አጥቶ አደጋ ላይ መውደቁን ለወላጆች ለማርዳት ዲፕሎማቱ እያሰሙ ያለው ጩሀት ተቀባይነት የሌለው እና ከ3000 በላይ የሆኑ ህጻናትን ሜዳ ላይ በትኖ ት/ቤቱን ለመዝጋት የሚደረገው ጥረት ከጀርባው ድብቅ አጀንዳ ያለው መሆኑ ይነገራል ።

ከዚህ ባሻገር ዘንድሮ የሳውዲ አረቢያ መንግስት ያወጣውን አዋጅ ለመተግበር ማንኛውም መምሀር የመኖሪያ ፈቃዱ በት/ቤቱ ሰር እንዲሆን ለማስቻል ት/ቤቱን በእጅ አዙር በባለቤትነት የተቆጣጠሩት ዲፕሎማቶች በጀመሩት ዘመቻ ከት/ቤቱ ካዝና አህዙ በትክከል የማይታወቅ ከፍተኛ የሆነ ገንዘብ ያለምንም ማስረጃ ህገወጥ በሆነ መንገድ ወጪ መደረጉን የሚገልጹት ለጉዳይ ቅርበት ያላቸው ወገኖች ለመምህራኑ ጉዳይ ማስፈፀሚያ ተመድቦል ተብሎ ለይስሙላ በቦርድ አባላቱ ከተነገረው 70 ሺህ ሪያል እና ለኮሚኒቲው ካፍቴርያ ድጎማ በብደር መልክ ተሰጥቷል ተብሎ ከት/ቤቱ ካዝና በሚስጠር ውጪ ከተድረገው ከ2 መቶ ዘጠናሺህ ሪያል ወይም « ከግማሽ ሚልዮን ብር » በተጨማሪ ቁጥሩ በወል የማይታውቅ ጥሬ ገንዘብ የት እንደገባ እና ለምን አገልግሎት እንደዋለ በግልጽ እንደማይታወቅ ይገልጻሉ ።
Saudi Arabia ethiopian school 2

ሳውዲ አረቢያ ውስጥ በተለያዩ ዝቅተኛ ስራዎች ላይ ተመደበው ከሚሰሩ የውጭ ሃገር ዜጎች ያነስ ደሞዝ እይተከፈላቸው የስደት አለሙን ህይወታቸውን ለማሸነፍ የሚባዝኑት የት/ቤቱ መምህራን እና ሰራተኞች የመኖሪያ ፈቃዶቻቸውን በት/ቤቱ ሰር ለማድረግ ከያንዳንዱ መመህራን የወር ደሞዝ እስከ ሁለትሺህ እና ከዛ በላይ መቆረጡን ያረጋገጡ ምንጮች መምህራኑ ህጋዊ ለመሆን ባላቸው ጉጉት ከሆድ ከማታልፍ ደሞዛቸው በየወሩ የህን ያህል ከፈሉ እይተባለ የሚጣልባቸው እዳ ከወር ደሞዛቸው ዝቅተኝነት ጋር ተዳምሮ በኖራቸው ያስከተለውን ቀውስ ለመታደግ ተጨማሪ ገቢ ፍለጋ በትርፍ ግዜያቸው የተለያዩ ተማሪዎችን በክፍያ በማስጠናት አሊያም ያለ እረፍት በተለያዩ የጉለብት ስራዎች ላይ ለምሰማራት መገደዳቸው በት/ቤቱ የመማር ማስተማር ሂደት ላይ አሉታዊ ተፀእኖ በማሳደሩ ወላጆች በት/ቤቱ ላይ የነበራቸው ተስፋ መጨለሙ ይነገራል። ይህ በዚህ እንዳለ የሳውዲ አረቢያ ት/ሚንስቴር መ/ቤት ቀደም ብሎ ማንኛውም ተቋም በስሩ ት/ቤቶችን መከፈት ከፈለገ ጥራቱን የጠበቀ በሳውዲ አረቢያ የት/ሚ/ር ህግ መሰረት የተለያዩ ማስፈርቶችን ያሞላ ከኪራይ ነጻ የሆነ የግል ህንጻ ሊኖረው እንደሚገባ ባወጣው መመሪያ መስረት በሪያድ አለም አቀፍ የኢትዮጵያ ኮሚኒ ት/ቤት ዲዛይኑ ለመጋዘን መዋል የሚገባው የመጸዳጃ እና የተማሪ እረፍት ቦታዎችን ያላሞላ ከመሆኑም በላይ ህጻናቱ ይማሩበታል የሚባለው ህንጻ በማርጀቱ በተማሪዎቹ ህይወት ላይ ሊያስከትል የሚችለውን አሰቃቂ አደጋ ከግመት በማስገባት የሳውዲ እሳት አደጋ መቆጣጠሪያ እና መከላከያ ከፍል ከሳውዲ ትምህርት ሚ/ር ጋር በመተባበር የት/ቤቱ ፈቃድ እንዲሰረዝ መወሰናቸውን ተከትሎ ት/ቤቱ በቀጣይ የትምህረት ዘመን የመማር ማስተማር ሂደቱን መቀጠል እንደማይቸል ከት/ቤቱ የሚወጡ ሚስጥራዊ መረጃዎች ያመለክታሉ ።

በሳንሆዜ አካባቢ ለምትኖሩ ኢትዮጵያውያን፡ ፋሲል ደመወዝ እና ደሳለኝ (ባላገሩ) ጁላይ 5 ሥራዎቻቸውን ያቀርባሉ (ፍላየር)

$
0
0

በሳንሆዜ ቤይ ኤሪያ ለምትገኙ ኢትዮጵያውያን ድምጻዊ ፋሲል ደመወዝ እና ደሳለኝ መልኩ (ባላገሩ) ጁላይ 5 ቀን 2014 ዓም በሳንሆዜ ካሊፎርኒያ ሥራዎቻቸውን ያቀርባሉ። አዘጋጆቹ ፍላየራቸውን በዘ-ሐበሻ ድረገጽ እንዲታተም ልከዋል – እንደሚከተለው አስተናግደናል
fasil demewez 1

Viewing all 15006 articles
Browse latest View live