Quantcast
Channel: Ethiopian News | ዘ-ሐበሻ | Latest News Provider | News For All
Viewing all 15006 articles
Browse latest View live

ኮተቤ መምህራን ኮሌጅ በተማሪዎች ተቃውሞ እየተናጠ ነው

$
0
0

Breking Newsኮተቤ መምህራን ኮሌጅ ቅጥር ግቢ ውስጥ ተማሪዎች ተቃውሟቸውን እያሰሙ ነው፤ ግጭት እንደተፈጠረም የሚያመላክቱ መረጃዎች እየወጡ ነው፡፡ ካለፈው ሳምንት ጀምሮ በወለጋ፣ጅማ፣መቱ፣አዳማ እና አምቦ ዩኒቨርሲቲዎች የኦሮሞ ተማሪዎች አዲሱን የአዲስ አበባ ማስተር ፕላን በመቃወም ተቃውሞ ማሰማታቸውና የፀጥታ ሀይሎችም ከፍተኛ ድብደባ እንዳደረሱባቸው ይታወሳል፡፡


ሰማያዊ ፓርቲ የአርበኞችን ቀን ሊያከብር ነው –በተጨማሪም የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮችና አባላት ቅጣት ተጣለባቸው

$
0
0

ሰማያዊ ፓርቲ ሚያዝያ 27/2006 ዓ.ም የአርበኞችን ቀን በጽ/ቤቱ ታዋቂ የታሪክ ተመራማሪዎችንና ሌሎች ምሁራንን ጋብዞ እንደሚያወያይ ምክትል የህዝብ ግንኙነቱ አቶ እምላዕሉ ፍስሃ ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡

ምክትል የህዝብ ግንኙነቱ እንዳስታወቁት ስነ ስርዓቱ ሰኞ ሚያዝያ 27 ከጠዋቱ 3 ሰዓት የሚጀምር ሲሆን ማንኛውም ኢትዮጵያዊ በፕሮግራሙ መሳተፍ ይችላል ብለዋል፡፡ ‹‹የስነ ጽሁፍ ተሰጥዖ ያላቸውና በበዓሉ ስራቸውን ማቅረብ የሚፈልጉ ኢትዮጵያውያንንም  እንዲሳተፉ እንፈልጋለን ያሉት ኃላፊው›› ፕሮግራሙን ወጣቶች ስለ አባቶቻቸው ታሪክ እንዲያውቁ ከማድረግም ባሻገር ስራቸውን በማስታወስ ታካቸውን ለመዘከር እንደሚፈልጉ አክለው ገልጸዋል፡፡

 

የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮችና አባላት ህግን ለማስከበር በመጣራቸው ተጨማሪ ቅጣት ተጣለባቸው

ethiopia-blue-party-300x164ሚያዝያ 19/2006 ዓ.ም ለተካሄደው ሰላማዊ ሰልፍ በቅስቀሳ ላይ የታሰሩት የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮችና አባላት በ1000 (አንድ ሺህ ብር) ዋስ እንዲወጡ መወሰኑን ተከትሎ ‹‹እኛ ነጻ ነን፡፡ ገንዘብ አስይዘን እንወጣም፡፡ ስራችን ህግ ማስከበር እስከሆነ ድረስ እየታሰርንም ቢሆን ህግ እናስከብራለን፡፡ በመሆኑም ነጻ እስካልተለቀቅን ድረስ እሰሩን፡፡›› በማለታቸው ተጨማሪ ክሶችና ቅጣቶች እየተጣለባቸው ነው፡፡ በትናትናው ዕለት ሜሮን አለማየሁና ትግስት ወንዲፍራው ‹‹ግቢ በመረበሸ›› ተጨማሪ ክስ መከሰሳቸው ይታወቃል፡፡ በአሁኑ ወቅት በቤላ ፖሊስ ጣቢያ የሚገኙ 14 ያህል የሰማያዊ ፓር አመራሮችና አባላትም ተመሳሳይ ክስ የተመሰረተባቸው ሲሆን ባለፈው ከፍላችሁ ውጡ ከተባሉት 1000 (አንድ ሺህ ብር) በተጨማ 600 (ስድስት መቶ ብር) ጨምረው ከፍለው እንዲወጡ ተፈርዶባቸዋል፡፡

እነዚህ አመራሮችና አባላት መጀመሪያ የካ ፖሊስ ጣቢያ ታስረው የነበሩ ቢሆንም እስረኛውን በማሳመጽና በመረበሽ ከመከሰሳቸውም በተጨማሪ ወደ ቤላ ፖሊስ ጣቢያ ተዛውረዋል፡፡ በወቅቱ ድብደባና ማዋከብ እንደደረሰባቸው የሚናገሩት ታሳሪዎቹ ‹‹ህግን ለማስከበር የምናደርገውን ጥረት እንደ ህገ ወጥነት ተቆጥሮ ተጨማሪ ክስና በደል ቢፈጸምብንም እኛ ህግ ማስከበራችንን እንቅጥላለን›› ብለዋል፡፡

በተመሳሳይ በጉለሌ ፖሊስ ጣቢያ የሚገኙትና ዛሬ ስምንት ሰዓት ላይ ፍርድ ቤት የቀረቡት የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮችና አባላት እያንዳንዳቸው 5500 ብር አስይዘው እንዲወጡ ተፈርዶባቸዋል፡፡ ታሳሪዎቹ ይህንን ውሳኔ በመቃወም ‹‹ነጻ ካልተለቀቅን አንወጣም!›› ያሉ ሲሆን ከዳኛው የተሰጣቸው መልስ እንዳሳዘናቸው ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡  ‹‹ዳኛውና አቃቤ ህጉ ተመካክለው ነው የገቡት፡፡ በእያንዳንዳችን 5500 ብር እንድንከፍል ሲፈርዱ፤ ‹እኛ ተማሪዎችና የመንግስት ሰራተኞች ነን ከየትም አምጥተን መክፈል አንችልም!› አልናቸው፡፡ እነሱ ልክ አንድ ሰው እቃ ሲገዛ እንደሚከራከረው ‹በቃ! 2000 ብር ይሁንላችሁ› አሉን፡፡›› ያሉት ታሳሪዎቹ በህግ ሳይሆን በዘፈቀደ እየተሰራ መሆኑ አሳዝኗቸዋል፡፡ በሌላ በኩል  ‹‹ህገ ወጥ ቢሆንም በሌላ አካባቢ የታሰሩት የእኛ ጓደኞች 1000 ብር ነው እንዲከፍሉ የተወሰነባቸው፡፡ የእኛውን ለምንድን ነው 5500 ያደረጋችሁት?›› ብለው ሲጠይቁ ዳኛው ‹‹ቅጣቱ ከጣቢያ ጣቢያ ይለያያል፡፡›› የሚል አስገራሚ መልስ እንደሰጧቸው ገልጸውልናል፡፡

ከአዲስ አበባ ፕላን ተማሪዎቹ አይቀድሙም?

$
0
0
ዳዊት ሰሎሞን

2_nበዛ ካሉ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት እየሰማናቸው የምንገኛቸው ዜናዎች አስደንጋጭ ናቸው፡፡ለነገሩ ገዢው ፓርቲ የሚከተለው ሩሲያን ከመፈረካከስ ያላደነ የፖለቲካ መስመር እንዲህ አይነት ፍሬ ማፍራቱ የማይጠበቅ አልነበረም፡፡እናም የኦሮሞ ተወላጅ የሆኑ ተማሪዎች የአዲስ አበባ አካባቢዎችን ወደ አዲስ አበባ ይጠቀልላል የሚል ስጋት ባሳደረባቸው የከተማይቱ ማስተር ፕላን ላይ ያላቸውን ተቃውሞ ለመግለጽ የተቃውሞ ሰልፎችን ለማድረግ ዝግጅት አጠናቅቀው ወደ ትገበራው ሲያመሩ ግጭት ተፈጥሮ በዛ ያሉ ተማሪዎች መጎዳታቸውን ሰምቼያለሁ፡፡


በእኔ እምነት ማስተር ፕላኑን ያዘጋጀ አካል ፊት ለፊት ቀርቦ ለመነጋገር ስህተት ከተሰራም እርማት ለመውሰድ ለምን እንደማይደፍር አይገባኝም፡፡መቼም ተማሪዎቹ ተቃውሞ ያቀረቡት መሬታችን ተቆርሶ ለባዕድ አገር ሊሰጥብን ነው በማለት አይመስለኝም፡፡ስጋታቸው ቤተሰቦቻቸው ከያዟት ኩርማን መሬት ጋር የሚጋመድ ይመስለኛል፡፡ ነገ ቤተሰቦቻቸቸው የያዟትን ኩርማን መሬት በሊዝ ለአንዱ ባለ ጊዜ ተሰጥታ ፎሪ እንዳይወጡ ሳይሰጉ አልቀሩም፡፡ይህንን ስጋት በፖሊስ ቆመጥና በፌደራል መሳሪያ ማስወገድ ይቻላል እስካልተባለ ድረስ መነጋገር መቅደም ይኖርበታል፡፡


እባካችሁ ለንግግር ዕድል ስጡ፡፡

በአንድነት ፓርቲ የሰላማዊ ሰልፍ ጥሪ ላይ ዘመቻ ተከፍቷል

$
0
0

ዳዊት ሰሎሞን


በአዲስ አበባ ከተማ ያለውን የኢኮኖሚ፣የማህበራዊና ፖለቲካዊ ችግሮች በተመለከተ የከተማይቱ ነዋሪ አደባባይ በመውጣት ድምጹን ከፍ ባለ መንገድ በዕሪታ እንዲያሰማ አንድነት ፓርቲ ለፊታችን እሁድ ጥሪ እያደረገ ይገኛል፡፡ነገር ግን ጥሪው በመብራት መጥፋት፣በንጹህ ውሃ አለመኖር፣በትራንስፖርት፣በቴሌ ኮም ኢንዳስትሪው ኋላ ቀርነት
ብቻ እንደሆነ በማስመሰል ለማንከኳሰስ የሚደረጉ ዘመቻዎች በፓርቲው ላይ ተከፍተዋል፡፡


እርግጥ ነው ለአንድነት
የኑሮ ውድነት፣የስራ አጥ ቁጥር መበራከትና እንደ ንጹህ ውሃ ፣መብራትና የቴሌ ኮም አገልግሎት ደካማነት አነገብጋቢ ጉዳዮች ተደርገው መወሰድ እንደሚገባቸው ያምናል፡፡
ሰልፉ ግን ከላይ ለመጥቀስ ከሞከርኳቸው ዐቢይ ጉዳዮች በተጨማሪ ‹‹የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ይመለከታል፡፡
የመልካም አስተዳደር እጦት ለእርስዎ ምንድን ነው?
የቢሮክራሲው መንዛዛት፣ሙስናው ፣ፍትህ ማጣቱ፣አድልዎ መደረጉ፣ስራ ለመቀጠር የድርጅት አባልነት መስፈርት መደረጉ፣በአስተሳሰብዎ የተነሳ ልዩነት እየተደረገብዎ መሆኑ፣የኑሮ ውድነቱ፣አፈናው፣እስራቱ ወዘተ አ

179

በቃሊቲ እና በዝዋይ የሚገኙ ታሳሪዎች የርሀብ አድማ ሊያደርጉ ነው!!

$
0
0

MillionsVoice1በቃሊቲ እና በዝዋይ የሚገኙ ታሳሪዎች የርሀብ አድማ ሊያደርጉ ነው!! ህዝቡ በነቂስ በመውጣት የእሁዱን ሰላማዊ ሰልፍ እንዲቀላቀል ጥሪ አቅርበዋል!! በቃሊቲና በዝዋይ ማረሚያ ቤቶች በግፍ ተፈርዶባቸው በእስር ላይ የሚገኙ የህሊናና የፖለቲካ እስረኞች አንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ‹‹የእሪታ ቀን ›› በሚል መሪ ቃል የሰየመውና እሁድ ሚያዝያ 26 ቀን 2006 ዓ.ም የጠራውን ህዝባዊ ሰላማዊ ሰልፍ በማስመልከት ከህዝብ ጎን ሆነን ድምፃችንን እንዳናሰማ በግፍ የተወረወርንበት እስር ቤት ቢያግደንም ከአርብ ጀምሮ ሰላማዊ ሰልፍ እስከሚደረግበት እለት ድረስ የርሀብ አድማ በማድረግ ከህዝቡ ትግል ጎን በመቆም አጋርነታችንን እናሳያለን ሲሉ ለፍኖተ ነፃነት ገለፁ፡፡ ህዝቡ ከየቤቱ በነቂስ በመውጣት ሰላማዊ ሰልፉን እንዲቀላቀልም ጥሪ አቅርበዋል፡፡

Millions of voices for freedom – UDJ

ጋዜጠኛ ነብዩ ኃይሉና የአንድነት የአዲስ አበባ ሰብሳቢ አቶ ዘካሪያስ የማነብርሃን ታሰሩ –ፖሊስ ህገ ወጥ እስሩን ቀጥሏል

$
0
0
ዳዊት ሰሎሞን
ጋዜጠኛ ነብዩና የአንድነት ሊቀመንበር ታሰሩ
ጋዜጠኛ ነብዩ ሃይሉ የቀስቃሾቹን እንቅስቃሴ ለመዘገብ በወጣበት ለእስር ተዳርጓል፡፡በካዛንቺስ ፖሊስ ጣብያ ከነብዩ ጋር የአዲስ አበባ የአንድነት ሊቀመንበር ዘካሪያስ የማነብርሃንና ዘላለም ደበበ ይገኙበታል፡፡የጣብያው ኃላፊዎች ‹‹ቤተ መንግስት አካባቢ ቀስቅሳችኋል››የሚል ውንጀላ አቅርበውባቸዋል፡፡

ፖሊስ ህገ ወጥ እስሩን ቀጥሏል አንድነቶችም በእስሩ አልበረገጉም

ከአዲስ አበባ መስተዳድር እውቅና ለተቸረው ሰላማዊ ሰልፍ የአንድነት አባላት በራሪ ወረቀት በማደል፣ፖስተሮችን በመለጠፍና በመኪና ቅስቀሳ ሲያደርጉ የእውቅናው ደብዳቤ እውቅና ግልባጭ የደረሰው ፖሊስ አባላቱን በማሰር ስራ መጠመዱ አስገራሚ ቢሆንም የፓርቲው አባላት ቅስቀሳውን ከማድረግ አልተቆጠቡም፡፡
ፖሊሶቹ ለያዟቸው የአንድነት አባላት ወረቀት ለመበተን፣ፖስተር ለመለጠፍና የመኪና ላይ ቅሰቀሳ ለማድረግ ፈቃድ አምጡ በማለት ይጠይቃሉ፡፡ነገር ግን ለሰላማዊ ሰልፍ እውቅና ከሚሰጥ ወረቀት በስተቀር ለቅስቀሳ ተብሎ የሚሰጥ ወረቀት ባለመኖሩ የፖሊስን እስር አስገራሚም አስተዛዛቢም አድርጎታል፡፡ 
የአንድነት አባላት በአሁኑ ወቅት በካዛንቺስ፣በቦሌና ንፋስ ስልክ ፖሊስ ጣብያዎች ታስረው ይገኛሉ፡፡

61 10

 

miilion v 2

ጃዋር ነበር የሚለው፣ አሁን ግን የኦሮሞ ተማሪዎችም ደገሙት –ኦሮሚያ የኦሮሞዎች ናት (ናኦሚን በጋሻዉ)

$
0
0

ናኦሚን በጋሻዉ
naomibegashaw@gmail.com

 

በዉጭ አገር የሚኖሩ የኦሮሞ ብሄረተኖች፣ በዶር መራር ጉዲና የሚመራዉን ኦፌኮ ጨምሮ በርካታ የኦሮሞ ድርጅቶች እና አንዳንድ የኦሮሞ ሜዲያዎች ያቀረቡትን ጥሪ በመቀበልና አዲሱን የአዲስ አበባ ማስተር ፕላን በመቃወም ፣ የኦሮሞ ተማሪዎች በአንዳንድ ዩኒቨርሲቲዎች ተቃዉሞ ማሰማታቸው በስፋት ተዘግቧል።

መቅደም ያለበትን ላስቀድም። ተማሪዎቹ ጥያቄዎቻቸዉን ያነሱት ፍጹም ሰላማዊ በሆነ መንገድ ነው። በፌደራል ፖሊስ የደረሰባቸው ድብደባ ልብን የሚያቆስል ከመሆኑም ባሻገር  መወገዝ አለበት። በዚህ ጉድያ ላይ፣  ሌላ አቋም ይዞ የሚከርከር ካለ፣ ለሰብአዊነት ደንታ የሌለው ሰዉ ነው ብዬ ከማለፍ ዉጭ ብዙ የምለው አይኖረኝም።

የኦሮሞ ድርጅቶች ሆነ ተማሪዎች አዲሱን ማስተር ፕላን የተቃወሙበት ሁለት ጥንድ ምክንያቶች ሊኖሯቸው ይችላል ብዬ አስባለሁ። አንደኛው፣ በልማት ስም የኦሮሞ ገበሬዎች አግባብ በሌለው መልኩ መፈናቀል የለባቸውም የሚል ነው።

በልማት ስም፣ ወይንም የአንድ ቋንቋ ተናገሪ በመሆናቸው ምክንያት ሰላማዊ ዜጎችን የማፈናቀሉ ተግባር፣  ላለፉት ሃያ አመታት በአገራችን በስፋት ሲታይ የነበረ አሳዛኝ ክስተት ነው። እነዚህ የኦሮሞ ድርጅቶች፣  የኦሮሞ ገበሬዎች ለምን ተፈናቀሉ በሚል አሁን እየተከራከሩና እየጻፉ እንዳሉት፣ በኦሮሚያ ዉስጥ «ይሄ አገራችሁ አይደለም እየተባሉ» ዜጎች ሲባረሩና የዘር ማጽዳት ወንጀል ሲፈጸምባቸው፣ በሌሎች የኢትዮጵያ ግዛቶች በልማት ስም ቤቶች ሲፈርሱ»  ለምን ብለው ድምጻቸውን አሰምተውን ቢሆን ኖሮ ለነርሱ የበለጠ ከበሬታ ይኖረን ነበር።

የኦሮሞ ገበሬዎች በኦሮሚያ ዉስጥ በጂማ፣ በኢሊባቡር፣ በወለጋና  በመሳሰሉት   በኦሮሚያ ክልል መንግስት ተፈናቅለው መሬታቸው ለባለ ሃብቶች የተሰጠበት ሁኔታ  እንዳለ እናውቃለን። ገበሬዎቹን ሆነ ሌሎች ዜጎችን የማፈናቀል ተግባር፣ ከኦሮሞነት ጋር፣ ወይንም በአዲስ አበባ ስር ከመሆን ጋር የሚያገናኘው ነገር የለም። ዜጎችን በቅያቸው የማፈናቀሉ ጉዳይ መንግስት ከሚከተለው የመሬት ፖሊሲ ጋር የተገናኘ ነው። መሬት የመንግስት እስከሆነ ድረስ በኦሮሚያ ክልል አስተዳደሪ ትእዛዝ ይሁን፣ በአዲስ አበባ ከንቲባ ትእዛዝ ፣ ዜጎች በግፍ ፣ በቂ ካሳ ሳይከፈላቸው እንዳይፈናቀሉ የሚገታ ምንም ነገር የለም። ስለዚህ የሚበጀው ፣ የኦሮሞ ገበሬዎችን ጨምሮ ማንኛዉም ዜጋ የመሬት ባለቤት እንዲሆኑ መታገሉ ነው።

ሁለተኛው ተቃዉሞ የተሰማበት ምክንያት፣  በቀጥታ ተቃዉሞ እያሰሙ ካሉ የኦሮሞ ተማሪዎች ጋር በሃሳብ የሚያላትመኝ ጉዳይ ሆኖ ነው ያገኝሁት። «ኦሮሚያ የኦሮሞዎች ናት። ፊንፊኔ የኦሮሞዎች ናት»  የሚለው መፈክራቸው ፣ እጅግ በጣም መርዛማ ከመሆኑም የተነሳ አገሪቷን ወደ ከፋ የዘር ጦርነት የመዉሰድ አቅም ያለው ነው። ይህ አይነቱ ፖለቲካ ከዉጭ በነጃዋር ሞሃመድ እየተጠነሰሰ ሲሠራበት የነበረና፣ በየድህረ ገጹና ሶሻል ሜዲያዉ የተረጨ  ሲሆን  ይኸው ዉጤቱም በመጠኑም ቢሆን በአንዳንድ የኦሮሞ ተማሪዎች ሲንጸባረቅ ለማየት እየቻልን ነው። ይህ መርዝ በአስቸኳይ እንዲመክን ካልተደረገ፣ በኦሮሞዎች እና በአማራዎች፣ በኦሮሞዎች እና በጉሙዞች፣ በኦሮሞዎችና በሶማሌዎች፣ በኦሮሞዎች እና ከፊቾዎች …መካከል የዘር ግጭት በስፋት ሊሰራጭ ይችላል። ይህም ደግሞ በዋናነት የኦሮሞ ማህበረሰብን ከሌላው ጋር በማጋጀት ፣ በማህበረሰቡ ላይ ከፍተኛ ጉዳት ያመጣል።

ይህ አይነቱን ፖለቲካ ፊት ለፊት መጋፈጥና መቃወም ያስፈልጋል። ከአሁን ለአሁን የተቃወሙት አገዛዙን  ነው በሚል፣ ዝም ተብለው ሊታለፉ አይገባም።

«ኦሮሚያ የኦሮሞዎች ብቻ ናት። ኦሮሚያ እየተወረረች ነው ! ፊንፊኔ የኦሮሚያ ናት…» የመሳሰሉትን  ከፋፋይና ጠባብ መፈክሮች ሲያሰሙ የሰማናቸው እነዚህ የኦሮሞ ተማሪዎችና በዉጭ ያሉ የኦሮሞ አክራሪዎች፣ ከገበሬዉ የሰብአዊ መብት ይልቅ፣  ከሃያ አመታት በፊት በኦነግ እና በሕወሃት በኃይል በሕዝቡ ላይ የተጫነዉን የኦሮሚያ ካርታ፣ መለወጡ ያሳሰባቸው ነው የሚመስለኝ። ከአሁን ለአሁን አዲስ አበባ ከሰፋች፣ ማስተር ፕላኑ ከጸደቀ፣ ኦሮሚያ ለሁለት ትከፈላለች የሚል ፍርሃት ሳይገባባቸው እንዳልቀረ ነው። ምናልባትም ኦሮሚያ ሬፑብሊክን የመመስረት እድላችንን ያጨልምብናል የሚልም ስጋት ሊኖራቸውም ይችላል።

ነገር ግን አንድ የዘነጉት ነገር አለ። አብዛኞቻችን ዝም ስንልላቸው፣ እነርሱ የሚጩኹት ጩኸት የበለጠ ተሰሚነት ያገኝ እየመሰላቸው ነው። አዲስ አበባ ዋና ከተማችን ናት። ማስተር ፕላን ኖረም አልኖረም አዲስ አበባ ትሰፋለች። እስከአሁንም የሰፋችው ማስተር ፕላን ኖሮ አይደለም። አዲስ አበባ ኦሮሞዉ፣ ሱማሌዉ፣ ትግሬው፣ አማራዉም ፣ ድብልቁም ..ሁሉም ያለ ፍርሃትና ያለ ሰቀቀን የሚኖሩባት ከተማ ናት። አዲስ አበባ በኦሮሚያ እንዳሉሌሎች ከተሞች፣ ኦሮሞዎች ብቻ የሚመረጡበትና የሚመርጡባት፣ ሌሎች በሰቀቀን እንደ ሁለተኛ ዜጋ የሚኖሩባት፣ አፓርታይድ የሰፈነባት ከተማ አይደለችም። አዲስ አበባ የሁሉም ናት። ሕዝቡ ከሁሉም አቅጣጫ በአዲስ አበባ መኖር ይፈልጋል። በዘረኝነት አጥር መታጠር አይፈልግም። መሻሻል ይፈልጋል። ወደ አዲስ አበባም ይጎርፋል። በዚህም ምክንያት አዲስ አበባ አደገች። የሕዝቧም ቁጥር ጨመረ።

በቅርብ ጊዜ ዉጥ ናዝሬት እና አዲስ አበባ ፣ አዲስ አበባ እና ደብረ ብርሃን፣ አዲስ አበባና ወሊሶ፣ አዲስ አበባና አምቦ ይገጥማሉ ተቦ ይጠበቃል። ከአዲስ አበባ ናዝሬት ያለው ሰፊ መንገድ ተጠናቋል። በኢኮኖሚና በሕዝብ ለሕዝብ ትስስር አኳያ ካየነው ፣ አዲስ አበባ እና አዳማ ገጥመዋል ማለት ይቻላል።  አዲስ አበአ እየኖሩ ናዝሬት የሚሰሩ፣ ናዝሬት እየኖሩ አዲስ አበባ የሚሰሩ ቁጥራቸው እየበዛ ነው። በቦሌ ያለው ኤርፖርት ብቃት ስለሌለው ፣ አዲስ አይሮፕላን ማረፊያ በቴሲ ከተማ ሊሰራ ነው። ቴሲ፣ ሰበታን አልፎ በአዲስ አበባ እና በወሊሶ መሃከል ያለች ናት። ኤርፖርቱ ሲጠናቀቅ ፣ የዚያኑ ያህል የኢኮኖሚክ እንቅስቃሴውም ያድጋል። አካባቢዉ ከአዲስ አበባ ጋር ትስስሩ የበለጠ እየጨመረ ይመጣል። ይሄም ደግሞ የሆነው በማስተር ፕላኑ ምክንያት አይደለም። የሕዝብ እንቅስቃሴ ነው። የሕዝብ እንቅስቃሴን ደግሞ በአዲስ አበባ ዙሪያ እንደ በርሊን ግንብ አይነት ፣ ካልተሰራ ማቆም አይቻልም። እነርሱ የሕዝብን እድገት ማፈን፣ ህዝቡን በዘር አጥር አሸገው ማስቀመጥ ቢፈልጉም፣ ህዝቡ ግን አይሰማቸው። ተሸናፊ የሚሆኑት እነርሱ እርሳቸው ናቸው። (በነገራችን ላይ የዉሸት አፈታሪክ ላይ ተመርኩዘው የአኖሌን የጥላቻ ሃዉልት የገነቡ፣ ነገ የአዲስ አበባን ግንብ እንገባ ቢሉ የሚያስደንቅ አይሆንም)

እንግዲህ «አዲስ አበባ ለምን አደገች፣ ተወረርን» የሚለውን ጠባብ አመለካከት መያዝ ሳይሆን  የሚያዋጣዉ፣ «አዲስ አበባ በምታድግበት ጊዜ ሁሉንም በጠቀመና ፍትሃዊነት ባለዉ መልኩ ይሁን» በሎ መከራከሩ ነው። በተለይም ከላይ እንደገለጽኩት መሬት የመንግስት ነው በሚል ዜጎችን በኃይል የማፈናቀል  ተግባር እንዲቆም አስፈላጊዉን ግፊትና ጫና ማሳደሩ በጣም አንገብጋቢ ጉዳይ ነው። ይህ የዘር ወይንም የጎሳ ጉዳይ ሳይሆን የሰብአዊ መብት ጉዳይ ነው።

የኦሮሞ ተማሪዎችንም ሆነ ድርጅቶች የኦሮሚያ የዘር ጠባብ ጥያቄዎችን ማንገብ አቁመው፣ የሰብአዊ መብት ጥያቄዎች ያንግቡ እላለሁ። ያኔ እኛም ከጎናቸው እንቆማለን። አሁን ግን «ኦሮሚያ ለኦሮሞዎች» ካሉ መንገዱን ጨርቅ ያርግላቸው። እነርሱን ከማንም በላይ  የምንታገልና የምንቃወም እንጂ የምንደግፍ አንሆንም። አዲስ አበባ የሁላችንም ናት። ቡራዪ፣ ሰበታ፣ ለገጣፎ፣ አምቦ፣ ወለጋ፣ ኢሊባቡር የሁላችንም ናቸው።

 

 

አቶ አንዷለም አራጌ በቃሊቲ እስር ቤት የረሃብ አድማ ላይ ነው

$
0
0

Free Andualem

ፍኖተ ነፃነት

የአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) ም/ሊቀመንበርና የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ የነበረውና ‹‹ሽብርተኛ›› በሚል የእድሜ ልክ እስራት የተፈረደበት አቶ አንዷለም አራጌ በቃሊቲ እስር ቤት ከሌሎች እስረኞች በተለየ ሁኔታ እሱ ላይ ብቻ ትኩረት ተደርጎ መብቱ በመጣሱ፤ እንዲሁም በተፅእኖና ክልከላ ሰለባ በመሆኑ ከትላንት ጀምሮ የረሃብ አድማ ላይ መሆኑን ቃሊቲ የሚገኙ የፍኖተ ነፃነት ምንጮች ገለጹ፡፡


ክብርነቶ  በተናገሩበት  ሳመንት? (ከዳዊት ዳባ)

$
0
0

ከዳዊት ዳባ

Sunday, April 27, 2014

Commentሰኞ መያዚያ 13 2006  ባሌ ውስጥ የሁለት ንፁሀን ዜጎችን መገደል በመስማት ሳምንቱን ጀመርነው።  አገዳደላቸው    ወንጀላችሁን ከባድ ያደርገዋል። የመጀመርያው ልጅ በቁጥጥራችሁ ስር ነበር። በህግ አግባብ መጠየቅ ስትችሉ ነው በነጻ እርምጃ የገደላችሁት። አፉ ውስጥ ሽገጥ አስገብታችሁ ተኩሳችሁ። በሚቀጥለው ቀን ይህን ግፍ ዜጎች ስለተቃወሙ  ሌላ ዜጋ ደግሞ በቀን ብረሀን ገደላችሗል።

ማክሰኞ  መያዝያ 14 2006  አፋር ውስጥ አስር ንፁሀን ተገለዋል። ከቦታው ያንድ እህት ምስክርነት።” እኔ አራሴ  የቆምኩት ስምንት እሬሳ ላይ ነው። ይህ የመጀመርያ አይደለም። በየቀኑ አምስት ልጅ፤ ስድስት ልጅ፤ ሰባት ልጅ፤ ስምንት ልጆች እየቀበርን ነው። ገዳዬች ፌደራል ፖሊሶች ናቸው። እጅግ ለጆሮ በሚከብድና በሚያሳዝን ሁኔታ ልጆ መገደሉ ሳያንስ ነብሰ ጡር  እህትም በጽኑ ተጎድታለች። ይህቺ እህታችን ሳትሞትም አልቀረችም’”። በዚሁ ቀን ጋንቤላ ዲማ ላይ መከላከያ ሰራዊት አባለት አስገድደን ፍቶወት ካልፈጸምን ብለው ባስነሱት አንባጓሮ ከመከላከያ ሶስት ከፌደራል አንድ ሞተዋል። “ጋዜጠኛ መሳይ ዝሆኖች ሲጣሉ” ብሎ እንደገለጸው ይህ ገጠመኝ ቁጥሩ ከራት በላይ የሆኑ ንፁሀን ዜጎች ሂወት ያለአግባብ እንዲጠፋ አድርጓል  ። ህጋዊና ሰላማዊ በሆነ መንገድ የሚታገሉት ድርጅቶች ውስጥ ሰማያዊ ፓርቲ አስራ ስምንት አባላቱ ምንም ወንጀል ሳይሰሩ በዚሁ እለት ታስረውበታል።   የአገሪቷ ህግ ተቃውሞ ለማድረግ ፍቃድ የማያሻ መሆኑን ቢደነግግም በዚሁ እለት አንድነት  ፍቃድ ከለከልንህ ብላችሁታል።

እሮብ መያዝያ 15 ካመት በፊት ዴሬደዋ ላይ በተነሳ የእሳት አደጋ በተያያዘ የታሰረ ዳንኤል ጎሳ የሚባል ዜጋ አሰቃይታችሁ ገድላችሗል። ይህ ወገን ደብደባ ሲፈፀምበት ነበር። ለእሬሳ ምርመራ ፖሊስ ከቤተሰቡ ጋር ወደ አዲስ አበባ ተልኳል። የተላከው ፖሊስ ገዳዩ  እራሱ አለመሆኑ የታወቀ ነገር የለም።  የሬሳ ምርመራው አምስት ደቂቃ በማይሞላ ጊዜ ተጠናቋል። ሐኪምቤቱ የሬሳ ምርመራ ውጤት ቅጂውን እንኳ  ለቤተሰቡ አልሰጥም ነው ያለው። ባንፃሩ አባት አበበ ጎሳ ልጄን ገድሏል ብለው ከጠረጠሩት አካል ነው የምርመራውን ውጤት ያገኛሉ የተባሉት። አቶ አበበ ያላቸው አንድ  ልጅ ብቻ ነው። እሱኑ ነው የገደላችሁባቸው።  ልጅ የሙት ልጅ ነው። አባት በወንድ አቅማቸው  ብቻቸውን ሆነውና መከራ አይተው ያሳደጉት መሆኑን ተናግረዋል። እናንተ እንዳላችሁት እራሱንም ያጥፋ ወይ መረጃዎች እንደሚያሳዩት ይገደል በናንተ እጅ እያለ ስለሞተ መንግስቶት ተጠያቂነት አለበት።

ሐሙስ መያዚያ 16  ጎንደር ጪንጋ ላይ ዜጎች ሰላማዊ በሆነ ሁኔታ የመብት ጥያቄ ማንሳት ከጀመሩ ቀናቶች ተቆጥረዋል። ይህን ምክንያት አድርጋችሁ አራት ዜጎችን ገድላችሗል። እንዲሁ አንድ ፖሊስ ሞታል ሌላ ቆስሏል። ነዋሪው ተቃውሞ ሲያሰማ የነበረው መሳርያ ሳይዝ ስለነበር ህዝብ  ፖሊሶቹ እርስ በእራሳቸው ተጋዳድለዋል እያለ ነው። እነዚህ ፖሊሶች የሞቱትም ሆነ የቆሰሉት በየትኛውም መንገድ ይሁን ወናው ጉዳይ  እናንተ   በተሸነፋችሁ ጊዜ ወይ ከዛም በሗላ አልቻልንም ብላችሁ ስልጣን ስላለቃቅችሁና ሁሌም ችግሮችን ሁሉ  በምትፈቱበት የሀይልና ግጭት ያለበት መንገደ ምክንያት  ስለሆነ አሁንም ለነዚህም ዜጎች ሞትም በቀጥታ ተጠያቂ ናችሁ። በዚሁ እለት  የቆሰሉት ዜጎች ብዙ መሆናቸውና ባህር ዳር ሆስቢታል ልህክምና መግባታቸውን ሰምተናል።  አስራ ስድስት ተጨማሪ የሰማያዊ ፓርቲ አባላት ማታሰራቸውንም በዚህ ቀን ነው የሰማነው።

አርብ መያዚያ 17 የሰላማዊ ፓርቲ ሰላሳሶት አባላት ሊቀመንበሩን ጨምሮ መታሰራቸውን ሰምተናል። እነዚህ ዜጎች ያለምንም ጥፋት የታሰሩት  ለሰላማዊ ሰልፍ ህዘብን ሲቀሰቀሱ በነበረበት ጊዜ ነው። የጋዜጠኛ የሱፍ ጌታቸው ዘግናኝና ልታፍሩበት የሚገባ ግብራችሁን  የሰማንበትም ቀን ነው። የዞን ዘጠኝ ስድስት አባላትም መታሰራቸውን የሰማነው በዚሁ ሳምንት ነው። መብራት አገልግሎት ለረጅም ጊዜ እያገኘን አይደለም ያሉ የሽሮ ሜዳ አካባቢ ነዋሪዎችን አፍሳችሁ አስራችሗል።

ቅዳሜና እሁድ ዜና ሰለሌ ነው እንጂ ግድያው፤ እስሩ፤ ማንገላታቱ ይኖራል። ግፋችሁን በማጋለጥ እንኳ እኩል ልንራመድ አልቻልንም። ጨርሼ ሳለቀው ሌላኛው ሰኞ መጥቶ ይህም ሳምንት እንዲሁ በመገደል በማሰር በማሸበር መጀመሩን እየሰማው ነው። በቀጣይ ያንድነት ሰላማዊ ተቃውሞ አለ። የስልምና እምንት ተከታይ ወንድሞቻችን ጥያቄያቸውን ለማስመለስ የሚያደርጉት እንቅስቃሴ አለ። አስተዳድራችሁ አድሏዊ ሆኖ እያለ አዲስ አበባን እናስፋፋለን በሚል ደሀ ዜጎችን ከመሬታቸው ለማፈናቀልና ለማኝ ለማድርግ የዘየዳችሁት እቅድ መረረ ተቃውሞ ከዜጎች እየስነሳ ነው። ጎንደር፤ ጋንቤላ ባጠቃላይ በመላ አገሪቱ የለውጥ ፍላጎት እየተንቀለቀለ ነው። ሰንቱን ገድላችሁ፤ ስንቱን አስራችሁና አሰቃይታችሁ እንደምትወጡት የምናየው ይሆናል።

ይህን እንዳስብ ያደረገኝ ሰባቱንም ቀን በየቀኑ በግፍ ስለተገደሉ እንሰማባቸው የነበሩ ሳምንታት እጅግ ብዙ መሆናቸውን ስለታዘብኩ ነው። በሳምንት አምስቴ፤ ሶስቴ ወይ አንዴ መስማት የተለመደ ነው። የታሰረውን፤ ግፍና ስቃይ የተፈፀመበትን  ወይ ያሰደዳችሁትን ዜጋ ጨምረን እንይ ካልን ይህን አይነቱ ወንጀል ሳይፈፀምና እኛም ሳንሰማ ያሳለፍነው ቀን ማግኘት  አይቻልም። ይህ እንግዲህ የመገናኛ ሽፋን ለማግኘት የቻለው ብቻ  ተወስዶ ነው።

በእርግጥ ንፁሀን ዜጎችን መግደል ማሰር ማሰቃየት ማሰደድ ትግል ላይ እያሉም ያለቆቾ  ዋና ሞያቸው እንደነበረ ብዙዎች መስከረዋል። ሚኒልክ ቤተ መንግስት ከገባችሁ ሀያ ሶስትኛ አመታችሁ ላይ ናችሁ። ታዲያ ከሀያ ሶስት አመት በሗላ ዛሬስ ነጻ እርምጃን  ማቆም ቻላችሁ ወይ ነው ጥያቄው?።  የለመግባባቶችን፤ ልዩነትን ሳትገድሉን ዜጋውን ሳታሸብሩ መፍታት ትችላላችሁ ወይ ነው ጥያቄው?። ከላይ እንዳዩትና ልትክዱት የማያችላችሁ ይህ ችግር ከአመት አመት የሚጨምር እንጂ የሚቀንስ በጭራሽ አልሆነም። ስለዚህ መልሱ ባጭሩ አልቻላችሁም ነው። በእርግጥም ይህን የሀያሁለት አመት እብደት ላየ  መግደልና ግፍ መፈፀም እንዳትችሉ እስክናደርጋችሁ ወንጀላችሁ አይቆምም ብሎ ድምዳሜ ዜጋው ላይ ባይደርስ ሲፈጥረው ጅላንፎ ሆኖ ነው ማለት ይቻላል። እርሶ እራሶ ዘላለማዊ ከብርና ሞገስ ብለው ማሀላ ፈፅመው  ስልጣን ከያዙ በሗላ እንኳ ብዙ ንፅሀን ዜጎች በነጻ እርምጃ ተገለዋል። ያለጥፋታቸው ዜጎች በገፍ እየታሰሩና ስቃይ እየተፈፀመባቸው ነው። የታዘለች ህፃንም አልቀረላትም። ይህን አይነት መንግስታዊ ሽብር በሚፈፀምበት አገር ለአፍ ካልሆነ ፖለቲካ ማህደሩ ስፍቷልም ጠቧልም ብሎ መከራከር ልብ ድክም ማድረግ ነው።

በጠቅላላው የስልጣን ዘመናችሁ የፈፀማችሁት ፍጅት ቢወዳደር ከደርጉ የሚብስ ይመስለኛል። ምክንያቱም  በዚህ ደረጃና በማያባራ ሁኔታ በየቀኑ በግፍ ስለሚገደሉ ስለሚታሰሩ ሰቆቃ ስለሚፈፀምባቸው ንፁሀን ዜጎች በኔ እድሜ ያኔ አይሰማም ነበር። በርግጠኛነት ግን እስቲ ቦንብ አፈንድተን ሀያ ሰላሳ ሰው እንግደልና የዜጋውን ስሜት እናጥና ወይ ፖለቲካ እንስራበት ብለው ፍጅት የሚፈፅሙ መሪዎች አልነበሩም።” ጦርነት ሰርተን” የምትባለው አለቆቾ የሚወዷት የጫወታ አይነትን ማለቴ ነው።

ደርጉም አንባገነን ስርአት ስለነበር ሰፈራ የመሳሰሉ ግብታዊና ጎጂ እቅዶችን ተግባራዊ አድርጓል። ዜጎች ያልተስማሙባቸውና አምርረው የተቃወሟቸው ቢሆንም  እንደናንተ ያጉረመረመውን ሁሉ በገፍ መግደል ወና የቅዱ ማስፈፀሚያ  ግን አልነበረም።  ሰበብ አይሁን ለማለት ነው። ህንፃ ለመግንባት፤ መንገድ ለመስራት፤ አበባ ለመትከል  የንፁሀን ሂወት እስርና ስቃይ የግንባታዎቹ ሁሉ መሰረቱ እኮ ነው የሆነው።  ይህ የባህሪያችሁ ከመሆኑም በተጨማሪ ሁላችሁም ጋር ከፍተኛ የማስተዳደር እውቀት አለ ማለት ብቻ ነው የሚቻልው።

ክብር የሆነው ለሰው  ልጅ ሂወት የሚሰጠው ዋጋ ከፍተኛ በነበረበት ዘመን ዜጎች ግዛው ለምን ለምን ሞተ? ማርታ ለምን ለምን ሞተች ብለው ጉሮሮ ሊይዙ ይደርሱ እንደነበር ያውቃሉ። ዛሬ ከአንድ እስከ አስር ዝም ብሎ ዜናችን ነው። ለምን ተብሎ መጠየቅ አይደለም ገደሏቸው እኮ ተብሎም በቀጣይ አናወራበትም። ሀምሳ፤ መቶና ሶስት መቶ አዲስ ቁጥር አየደለም። ከዚህ በፊት አድርጋችሁታላ። ያዋጣል ካላችሁ ግን ለወደፊቱም በርቱ። ይህን በሚመስል እውነታ ውስጥ ጊዜና ሁኔታ ይመቻቻል። ያኔ  ገደላችሁ አይደለም ገላመጣቸሁ የስልጣናችሁን ፍፃሜ እንደሚያደርገው  እነግሮታለው።  ማወቅ ያለቦት የተለወጠ ነገር የለም ያው ኢትዬጵያዊ ነው።

በግሌ  ስልጣኑ የያዙ ለት ያደረጉትን ንግግሮትን ካዳመጥኩበት ጊዜ ጀምሮ ሁሌም ሳዮትም ሆነ ስሰማዎት አብሮአደጌን ሞዘዘኝን ነው የሚያስታወሱኝ። በዛኑ  ሰሞን በፃፍኩት ፅሁፍ ስለዚሁ ጉዳይ ልነግሮት ነበር። ሰው ናቸው የሚሉ ሲበዙ አልቸኩል ሊሆኑ ይችላሉ ብዬ ተውኩት። ይህን ክፍል ጎርጄ በሌላ ገፅ ላይ አኖርኩት። ዛሬ ኮፒ ፔስት ነው ያደረኳት። በርግጥ ሰበአዊነት ያለበትና ልጆቼ ተቆጡኝ። ፀለይኩኝም የምትለዋ ቃለ መጠይቆት አጭበርብራኝለች።

ልጆች ሆነን ከልጅነቱ ጀምሮ የመጨረሻ ገንገበት የነበረ ልጅ ነበር።  ለዚህ ልጅ የሆነ ጊዜ ላይ ይህን ባህሪውን ያየ ሌላኛው አብሮ አደጌ  ሞዘዘኝ ብሎ የቅጥል ስም አወጣለት። ገንገበቶች ገገማ ስለሆኑ   እንደተጠመቀበት ወይ እንደሰለጠኑበት ጉዳይ ነው ለመሀበረሰቡ  ጠቃሚም ጎጂም የሚሆኑት። አክራሪ የእምነት ሰው፤ ወይ ገገማ  ቀልደኛ፤  ጨካኝ መርማሪ ወይ ለእውነት  የሚሞት ዳኛ ወይ የሚያናድድ ሊስትሮ ጠራጊ ሊሆኑ ይችላሉ። ሞዘዘኝ ከፍ ሲል የሰፈር የጠብ ቡድን አገኘው። ከዛ  አንዷን ጡቷ ላይ በጩቤ ወጋት፤ እትዬ እንትናን በድንጋይ ፈነከታቸው። የዛን ሰፈር ልጅ በብረት ሰንሰለት ቀጠቀጠው። ብቻ ስሙ ባንዴ ዝነኛማ ተፈሪም ሆነ። የጠብ ቡድን ውስጥ ደግሞ ድርሻቸው ማካበድና ማሟቅ የሆነ አሉ። ሀይ ሀይ ስለበዛበት ሞዘዘኝ እስታ ሊል አልቻለም። ቆያይቶ  ተገደለ።

እርሶን ሳይ ትግሬ ተጋዳላዮች ምርጥ መጠቀሚያ ነው ከመንጋው መዘው ያወጡት እላለው። ገንገበቶችን  እንዲሞቃቸው በማድረግ ብቻ እንደፈለጉ ሊነዷቸው መቻላቸውን አውቀዋል። የዚህ አይነት ሰዎችን ምንም አይነት ወንጀል ማሰራት ቀላል ነው።  የሚፈልገው  ጎሽ አበጀህ፤ አቤት ድፍረት፤ ለርሶ ሲሆን ባለእራዩም እንዲህ ሊያሳምረው አይችልም ነበር። እስከዛሬም ተሳስተናል አይነት ሙገሳን መጨመር ነው።  በርግጠኛነት ከበቀደሙ የፓርላማ ውሎዎ መልስ ብዙዎች ይህን አይነት አስተያየት ሰጥተዎታል። ከዋኖዎቹ ለዚሁ ጉዳይ ተደውሎሎታል። ሙገሳ ያለበት ተመሳሳይ ነገርን ብለዎታል።  ለሁሉም መልክቴን ጠቅላይ ሚንስትሩ ሞዝዘውኛል።  ብዬ አቆማለው።

 

የሕግ አምላክ የሞተባት አገር፤ በሕገ መንግሥት ሳይሆን በወያኔ የጫካ ሕግ ለሃያ ዓመታት (ያሬድ ኃይለማርያም)

$
0
0

ያሬድ ኃይለማርያም

ከብራስልስ፣ ቤልጂየም

ሚያዝያ 23፣ 2006

Commentለከት ያጣው የወያኔ ጭካኔ እና የማይነጥፈው የሕዝብ ትእግስት ኢትዮጵያን ወዴት እየወሰዷት እንደሆነ አገሪቱ ዛሬ ያለችበት ውጥንቅጥ ሁኔታ በግላጭ ያሳያል። በመግደል አባዜ የተለከፉት የወያኔ ተጋዳላዮች ዛሬም መግደላቸውን ቀጥለዋል። ለይስሙላ በወረቀት ላይ የሰፈረው ሕገ-መንግስት እና በውስጥ የያዛቸው መሰረታዊ የሆኑ የሰብአዊ መብቶችና ነጻነቶች ለወያኔ ተጋዳላዮች ምናቸውም እንዳልሆነ በተደጋጋሚ እያሳዩን ነው። በአገሪቱ ውስጥ ያለው የሕግ ማእቀፍ (አንዳንዶቹ ሕጎች በራሳቸው የማፈኛ መሳሪያ ተደርገው የተቀረጹ መሆኑ ሳይረሳ) ለወያኔ ተጋዳላዮችና ተራ ካድሬዎች ሳይቀር ምናቸውም አይደለም። ሲሻቸው ይገድላሉ፣ ያፍናሉ፣ ይሰውራሉ፣ ባደባባይ ይደበድባሉ፣ ሺዎችን በየማጎሪያው ያሰቃያሉ፣ ያዋርዳሉ፣ ቅጥ ባጣ መልኩ ይሞስናሉ፣ ይሰርቃሉ፣ ይዘርፋሉ፣ ያስፈራራሉ፣ ሴቶችን ይደፍራሉ፣ ህዝብን ያሸብራሉ፣ ምኑ ቅጡ።

እንግዲህ የሕግ አምላኩ ሲሞት ሥርዓት አልበኝነት ይነግሳል፤ ዘራፊዎች ይበራከታሉ፣ ገዳዮች ባደባባይ ገድል ይጥላሉ፣ ሙሰኞች አገርን እና ሕዝብ ይቆጣጠራሉ፣ የአገር ሃብት ያሸሻሉ፣ በድሆች ጉሮሮ ላይ ቆመው በሃብት ይጨማለቃሉ። በዚህ ላይ ጎጠኝነት ሲታከልበት መላ ቅጡ ይጠፋል። ብዙዎቹ እየከሰሙ ያሉ አገሮች (failed states)እየተባሉ በየጊዜው የሚጠቀሱ አገሮች በእነዚህ ችግሮች ውስጥ የሚማቅቁ ናቸው። ወያኔም ለኢትዮጵያ የዋለላት አንዱ ትልቁ ነገር ከእነዚህ አገሮች ተርታ እንድትሰለፍ ማድረጉ ነው። እንደ ታላቅ ስኬት የሚቦተለክለት የዛሬዋ የኢትዮጵያ ልማት ውስጡ ሲገባ ላዩ አሮ ውስጡ ሊጥ እንደሆነ ዳቦ ስለመሆኑ ምንም ጥናትና የተለየ ምርምር ሳይጠይቅ 95% የሚሆነውን የአገሪቷን ሕዝብ ኑሮ ማየት በቂ ነው። አንጻራዊ በሆነ መልኩ በወያኔ ዘመን የመጀመሪያዎቹ አሥር አመት ውስጥ እንኳን የኢትዮጵያ ሕዝብ ያገኛቸው የነበሩትን እንደ መብራት፣ ውኃ፣ የጤና አገልግሎትና ሌሎች መሰረታዊ ፍላጎቶቹ ዛሬ ተነፍጓል። የደብል ዲጂት ልማታዊነት ነጠላ ዜማዎች በወያኔ እና ባጫፋሪዎቹ የአለም አቀፍ ‘የልማት’ ተቋማት ጆሮዋችን እሲደነቁር በሚዘፈንበት በዚህ ወቅት የኢትዮጵያ ሕዝብ አስከፊ በሆነ የኑሮ ዋስትና ማጣት ውስጥ ሆኖ የመከራ እንቆቆውን እየተጋተ ይገኛል። የእነዚህ የመሰረታዊ አቅርቦቶች በዚህ ደረጃ ላይ አቆልቁሎ መገኘት አንኳን የቀለም አብዮት፤ ሌላም መገለጫ የሌላቸው አመጾችንና እልቂትን ቢወልድና በአገሪቱን ወደ ከፋ ብጥብጥ ቢከት የሚገርም አይደለም። ይሁንና እንደ ወያኔ ያለ ክፉ፣ መረን የማያውቅ እና ጨካኝ ሥርዓት እድለኛ ሆኖ ሆደ ሰፊ፣ የማይቻለውን ሁሉ የሚችል፣ ጨዋና ታጋሽ ሕዝብ ሲጋጥመው ጭካኔውን እያበረታ፣ የአፈና ሰንሰለቱን እያጠበቀ፣ አባላቱን በአሃብት እያሞሰንነና እያጎለበተ ይንሰራፋል። የአገር መፍረስ ወይም አደጋ ላይ መወደቅ የራሳቸውን ጥቅም አደጋ ላይ እስካልጣለ ድርስ ግድ የማይሰጣቸው ጎጠኛ ፖለቲከኞችም በደሃው ሕዝብ ላይ ይሰለጥኑበታል፤ ይሰይጥኑበታልም።

ሰሞኑን በአገሪቱ ውስጥ የሚስተዋለው የፖለቲካ ድባብ ወያኔ ከመቼውም ጊዜ በከፋ ሁኔታ አገሪቱን የሚዘውርበት መሪ ከቁጥጥሩ ውጭ እንዳይወጣ እየተውተረተረ ያለ መሆኑን ነው። ለዚህም ይመስላል ሰላማዊ ሰልፍ ለማካሄድ ባንዲራና መፈክር ይዘው በተንቀሳቀሱ የፖለቲካ ፓርቲ አባላት፤ በተለይም የሰማያዊ ፓርቲ አባላትን አስሮ እያሰቃየ ያለው። ለዚህም ነው በማኅበራዊ ድኅረ ገጾች በተለያዩ አገራዊ ጉዳዮች ላይ የውይይት መነሻ ሃሳቦችን እያጫሩ ሕዝቡ እንዲወያይ ይጋብዙ የነበሩ የዞን 9 አባላትን ለቃቅሞ አጉሮ እያሰቃያቸው የሚገኘው። ይህም አልበቃ ብሎ ባለፉት ሦስት እና አራት ቀናት ውስጥ ሰላማዊ በሆነ መንገድ ጥያቄ (ጥያቄያቸው ምንም ይሁን ምን) እያቀረቡ ያሉ የኦሮሚኛ ቋንቋ ተናጋሪ ዩንቨርሲቲ ተማሪች ላይ የተለመደውን የጭካኔ እርምጃ እየወሰደ ያለው። ከተለያዩ መገናኛ ብዙሃን እንደተገለጸው ከሆነ በርካታ ተማሪዎች በታጠቁ ሃይሎች የጭካኔ እርምጃ ለከባድና ቀላል የአካል ጉዳት ተዳርገዋል። በተለይም በአንቦ ከተማ ተማሪዎች በግፍ ተገድለዋል። የወያኔ መንግሥት ሥልጣን ከያዘበት ጊዜ አንስቶ በተማሪዎች ላይ ተደጋጋሚ የጭካኔ እርምጃዎችን ወስዷል። በመላ አገሪቷ በወያኔ እርምጃዎች ከተጠቁት ተማሪዎች ውስጥ ግን ትልቁን ግፍ የተቀበሉት በኦሮሚያ ክልል ውስጥ የሚገኙ ተማሪዎች ስለመሆናቸው የሰብአዊ መብት ጥሰቶችን የሚመለከቱ ሪፖርቶች ይመሰክራሉ። በሥራዬ አጋጣሚ እኔም ይህን አረጋግጫለሁ።

ዛሬ ላለንበት ጠቅላላ አገራዊ ክሽፈት፣ ውርደት እና የመከራ ሕይወት ከላይ እንደጠቀስኩት ለከት ያጣው የወያኔ ጭካኔ እና አፈና፤ እንዲሁም የአለማችን ተጭባጭ ሁኔታ ብቻ ሳይሆን  የማይነጥፈው የሕዝብ ትእግስት እና ዝምታም ትልቁን አስተዋጾ አድርጓል። በኦሮሚያ ክልል በሚገኙ ተማሪዎች ላይ፣ በጋዜጠኞች ላይ፣ በሰብአዊ መብት ተሟጋቾች ላይ፣ በተቃዋሚ ፓርቲዎች አባላትና ደጋፊዎች ላይ፤ እንዲሁም በኃይማኖት መሪዎች ላይ እየደረሰ ያለውን ግፍና በደል በጋራ ልናወግዘው እና ልንታገለውም ይገባል። በፍትሕ እና በኢ-ፍትሐዊነት፣ በጭቆና እና በነፃነት  መካከል ገለልተኛ ሆነው የሚንጠለጠሉበት ገመድ ወይም የሚቆዩበት ደሴት የለም። ፍትሕ ሲጓደል እያዩ እንዳላዩ መሆን በራሱ ኢ-ፍትሐዊነት ነው። መብት ሲጣስ እያዩ እንዳላዩ መምሰል በራሱ የጣሹ ግራ እጅ መሆን ነው። ንጹሃን ዜጎች በግፍ ሲገደሉ፣ ሲደበደቡ፣ ሲታሰሩ እና በሃሰት ክስ እየተፈረደባቸው በእስር ሲማቅቁ እያዩ ገለልተኛ መሆን አይቻልም። የፖለቲካ ገለልተኝነትን እና ለፍትሕ፣ ነጻነት እና ለህሊና መቆምን ባናምታታቸው ጥሩ ነው።

 

ለፍትህና ለነፃነት በመቆም የሰውነትም፤ የዜግነትም ግዴታችንን እንወጣ!

http://humanrightsinethiopia.wordpress.com/

ማኅበረ ቅዱሳን የጠራውና በጠቅላይ ቤተ ክህነቱ ጽ/ቤት የተፈቀደው ጉባኤ በፓትርያርኩ ውሳኔ ተከለከለ

$
0
0
  • Mhbere Kidusanዛሬ ሚያዝያ ፳፫ ቀን ፳፻፮ ዓ.ም. ከቀኑ 8፡00 – 11፡00 በኢትዮጵያ ብሔራዊ ሙዝየም አዲሱ አዳራሽ ‹‹ጥንታዊ የብራና መጻሕፍት ዓይነትና የይዘት ትንተና እንዲሁም አያያያዝና አጠባበቅ›› በሚል ርእስ የተጠራው የጥናት ጉባኤ ክልከላ መንሥኤ ‹‹የሥልጣን ተዋረድንና የዕዝ ሰንሰለትን ባልተከተለ መልኩ በቀጥታ የአድባራትንና የገዳማትን አስተዳዳሪዎችና ሠራተኞች እንዲሁም በቤተ ክርስቲያኒቱ ዙሪያ ጉዳዩ የሚመለከታቸውን ስብሰባ መጥራት›› የሚል ነው፡፡
  • ለጥናታዊ ጉባኤው የተጠሩት የገዳማትና አድባራት አለቆች ቤተ መዘክር ያላቸው ሦስት አብያተ ክርስቲያን ብቻ መኾናቸውን የገለጹት የጉባኤው አስተባባሪዎች በበኩላቸው÷ ማኅበሩ ለቤተ ክርስቲያን አባቶች፣ ጉዳዩ ለሚመለከታቸው ባለድርሻዎች፣ ምሁራንና እንግዶች ጥሪ ያደረገው ዕቅዱና አስፈላጊነቱ ለብፁዕ ዋና ሥራ አስኪያጁ ቀርቦ ከተመከረበትና ከተፈቀደ በኋላ መኾኑን አስታውቀዋል፡፡
  • ፓትርያርኩ ማኅበሩ በቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔ መሠረት ለብፁዕ ዋና ሥራ አስኪያጁ ተጠሪ የኾነበትን አሠራር በመሻር ማንኛውንም ስብሰባዎቹንና ጉባኤዎቹን ኹሉ ያለልዩ ጽ/ቤታቸው ፈቃድ እንዳያካሒድ ከሕጉ ውጭ በቀጥታ ለማኅበሩ የዋናው ማእከል ጽ/ቤት በላኩት የልዩ ጽ/ቤታቸው ደብዳቤ አሳስበዋል፡፡
  • የፓትርያርኩ ልዩ ጽ/ቤት የጥናታዊ ጉባኤውን መከልከል በተመለከተ በቀጥታ ለማኅበሩ የዋናው ማእከል ጽ/ቤት ደብዳቤ ለመጻፍ የተገደደው፣ የጠቅላይ ቤተ ክህነቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ ብፁዕ አቡነ ማቴዎስ ስለጉባኤው እንደሚያውቁና ዝግጅቱም የአሠራር ክፍተት እንደሌለበት ለልዩ ጽ/ቤቱ የበላይ ሓላፊ በማሳወቅ ሊታገድ እንደማይገባው በመከራከራቸው ነው፡፡
  • ሕገ ቤተ ክርስቲያኑ የዋናውን መሥሪያ ቤት ማለትም የጠቅላይ ቤተ ክህነቱን መምሪያዎችና ድርጅቶች ጨምሮ በቤተ ክርስቲያኒቱ ሥር የሚገኙትን የሥራ ዘርፎች ኹሉ በበላይነት የማስተዳደር ሥልጣንና ተግባር የሚሰጠው ለጠቅላይ ሥራ አስኪያጁ ነው፡፡ በዚኽ ረገድ የፓትርያርኩ ሓላፊነት በቅዱስ ሲኖዶስ የሚወጡ ሕጎችን፣ ደንቦችንና መመሪያዎችን በፊርማቸው የማስተላለፍ፣ በተግባር ላይ መዋላቸውንም መከታተልና መቆጣጠር ነው፤ ፓትርያርኩ የሚፈጽሟቸው ተግባራት ካሉም ዓበይትና የቅ/ሲኖዶሱ ውሳኔ ያረፈባቸው መኾን እንደሚገባቸው ተደንግጓል፡፡
  • በፓትርያርኩና በብፁዕ ዋና ሥራ አስኪያጁ መካከል ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የሥራ አለመግባባቶች እየተባባሱ የመጡ ሲኾን መንሥኤውም÷ በአማሳኞችና ጎሰኞች የሚመከሩት ፓትርያርኩ የማኅበረ ቅዱሳንን አገልግሎት ጨምሮ የጠቅላይ ቤተ ክህነቱን የሥራ ዘርፎች በቀጥታ የመምራትና የማስተዳደር ሓላፊነት ያለባቸውን ብፁዕ ዋና ሥራ አስኪያጁን በመጋፋት የጀመሩት አካሔድ ነው፡፡
  • ፓትርያርኩ የሚመለከታቸውንና የማይመለከታቸውን ዐውቀውና ለይተው በብቃት የመምራት አቅም ያጡትን ያኽል በዙሪያቸው የከተሙ አማሳኞችንና ጎጠኞችን መሸጋገርያ ያደረገውን ውጫዊ ተጽዕኖ በቀጥታ ተቀብሎ ለማስፈጸም የሚታይባቸው ፍጥነትና ታዛዥነት በእጅጉ እንዲናቁና እንዲጠሉ እያደረጋቸው ይገኛል፡፡

*                           *                              *

  • ጥናታዊ ጉባኤው÷ ማኅበረ ቅዱሳን በመተዳደርያ ደንቡ መሠረት ስለ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ልማት፣ ዕድገት፣ ታሪክ፣ ቅርስና መሰል አርእስተ ጉዳዮች ጥናት የሚያደርጉ ሰዎችን በተለይም ወጣት ምሁራንን ለማበረታታትና በተቻለው ኹሉ ለመርዳት፤ ሃይማኖታቸውን የሚጠብቁ፣ ቤተ ክርስቲያናቸውን የሚከባከቡና ሀገራቸውን የሚወዱ ብቁ ዜጎችን ለማፍራት በተጣለበት ሓላፊነት መሠረት ከቤተ ክርስቲያን ጋራ ተያያዥነት ባላቸው ሃይማኖታዊና ማኅበራዊ ርእሰ ጉዳዮች ላይ ጥናትና ምርምር ለማከናወን ባቋቋመው የጥናትና ምርምር ማእከል በየኹለት ወሩ የሚካሔድ መደበኛ መርሐ ግብር ነው፡፡
  • የማኅበሩ የጥናትና ምርምር ማዕከል በየኹለት ወሩ የሚያካሒደው መደበኛ ጥናታዊ መድረክ አካል የኾነውና የሚመለከተው የብፁዕ ዋና ሥራ አስኪያጁ ጽ/ቤት ዝርዝር ይዘቱን ከአንድ ወር በፊት በጋራ ውይይት ጭምር እንዲያውቀው ተደርጎ የተጠራው ጥናታዊ ጉባኤ፣ በጥንታዊ የብራና መጻሕፍት ዓይነትና የይዘት ትንተና እንዲኹም ጥበቃ ላይ ያተኮረ መኾኑ የመርሐ ግብሩ መግለጫ ያመለክታል፡፡par
  • ሊቀ ጠበብት አክሊለ ብርሃን ወልደ ቂርቆስ ‹‹ዜና መጻሕፍተ ብራና›› በተሰኘውና በ፲፱፻፷፮ ዓ.ም. በተካሔደው ሦስተኛው የኢትዮጵያ ዓለም አቀፍ ጥናት ጉባኤ ላይ ባቀረቡት ጽሑፋቸው እንደገለጹት÷ ጥንታዊ የብራና መጻሕፍታችን ገበታቸው የወርቅ የኾነ፣ የብርዓቸው አጣጣልና የብራናቸው ንጽሕና፣ የቅርፃቸው ማማርና ውበት ሲመለከቱት በእውነት የእነርሱን መልክና ቅርፅ የኑሮ ቤት አድርጎ መኖር እንጂ በዚኽ ዓለም በሥጋዊ ኑሮ ታስሮ መኖርን አያስመኙም፡፡
  • ከቅዱሳን ገድላትና ድርሳት ባሻገር አያሌ ‹የቴዎሎጊያ እና ፊሎሶፊያ› ሀብት ያካበቱት ጥንታዊ የብራና መጻሕፍት በይዘታቸው ‹‹እግረ ኅሊና ያልደረሰበት፣ የአእምሮ ክንፍ ያልበረረበት የተሸሸገ ጥበብና ያልተሞከረ ስውር ፍልስፍና›› የተካበተባቸው ናቸው ያሉት ሊቁ÷ ያልተከፈተውን የዕውቀት ጎዳና፣ ዓይን ያላየውን ዦሮ ያልሰማውን በጥበበኞች ያልታሰበውን ብልሃትና ሥነ ጥበብ መፈለግና መሻት ፈልጎም ማግኘትና አግኝቶም በፍሬውና በመልኩ መጠቀም ከአኹኑ ትውልድ የሚጠበቅ አዲስ አለኝታ፣ አዲስ ተስፋ፣ አዲስ የምሥራች መኾኑን አመልክተዋል፡፡
  • የተማረው ትውልድ የጠፋባትን የወርቅ ቀለበት ለማግኘት ባጡ፣ ቆጡ፣ ማዘንቱ፣ ማቶቱ ሳይቀር ኹሉንም በጥንቃቄ እያገላበጠች የምትፈልገውን ልባም ሴት መምሰል እንዳለበት ሊቁ በጽሑፋቸው መክረዋል፡፡ የበሬ ቆዳው በገዛ ሞራው እንዲለፋና እንዲለሰልስ የሀገራችን መልክና ቅርፅ በገዛ ሥነ ጽሑፋችንና ቅርፃችን ማሣመር እንድንችልና በዝግ ቤት ከየቤተ መቅደሱ ምህዋርና ከዋሻ ውስጥ ወይም ከመንደርና ደንበኛ ካልኾነ ዕቃ ቤት ተደብቆ ትውውቁ ከሌሊት ወፍና ከአይጥ መንጋ ጋራ የኾነውን የአባቶቻችንን ሥነ ጽሑፍ እያሠሥንና እየመረመርን ለተከታዩ ትውልድ እንድናቆይም በጥናታቸው አደራ ብለው ነበር፡፡
  • የጠቅላይ ቤተ ክህነቱ መምሪያዎች የበጀት እጥረትንና የሰው ኃይል ውሱንነትን በመጥቀስ ተግባራቸውን ማከናወንና የታሰበውን ለውጥና ውጤት ማምጣት እንደተሳናቸው ሰሞኑን በአስተዳደር ጉባኤው ላይ ቀርቦ ከተገመገመው የስድስት ወር ዕቅድ ክንውን ሪፖርታቸውበተረዳንበት ኹኔታ ያልነበሩና የሌሉ ለመኾን የተቃረቡትን ጥንታዊ የብራና መጻሕፍታችን ላይ ያተኮረው ጥናታዊ ጉባኤ የተከለከለበት ዋነኛ ምክንያት ታድያ፣ በልዩ ጽ/ቤቱ ደብዳቤ እንደተመለከተው ዝግጅቱን ካለማወቅ አልያም የዝግጅት ሒደቱ የሥልጣን ተዋረድንና የዕዝ ሰንሰለት አልተከተለም ከሚለው የተለመደ የማሰናከያ ስልት ጋራ በርግጥም የተያያዘ እንዳልኾነ ግልጽ ነው፡፡
  • የልዩ ጽ/ቤቱ የክልከላ ውሳኔ ከታወቀበት ከትላንት ቀትር ጀምሮ ደብዳቤውን እያሰራጩ የሚገኙት በፓትርያርኩ ዙሪያ በአማካሪነትና ረዳትነት ስም ከተጠጉት እነንቡረ እድ ኤልያስ ኣብርሃ ጋራ የዓላማና የጥቅም ግንኙነት ፈጥረው የሚንቀሳቀሱት አማሳኞቹ እነኃይሌ ኣብርሃ መኾናቸው ሲታይ የክልከላ ውሳኔው ምንጭ፣ የአብነት መምህራን ሀገር አቀፍ ጉባኤ ከታገደበት የካቲት ወር ጀምሮ የተጠናከረውና ማኅበሩን ብሎም ቤተ ክርስቲያኒቱን የማዳከም ልዩ ተልእኮ ባላቸው ባለሥልጣናት ጭምር ተደግፎ የቀጠለው ጫና ስለመኾኑ ግልጽ ያደርገዋል፡፡
  • የማኅበሩ አመራር ስለፓትርያርኩ ልዩ ጽ/ቤት የክልከላ ደብዳቤ ከብፁዕ ዋና ሥራ አስኪያጁ ጋራ መምከሩ የተገለጸ ሲኾን በብፁዕ ዋና ሥራ አስኪያጁ አማካይነት የጽሑፍ ምላሽ እንደሚሰጥ ተመልክቷል፤ የጎሰኝነት ሰለባ በመኾንና ለአማሳኞች ሽፋን በመስጠት በበታች ሠራተኞች ዘንድ ሳይቀር ክፉኛ እየተናቁና እየተጠሉ በመጡት ፓትርያርክ ዙሪያ የተኮለኮሉትን ጥቅመኞች የማጋለጥ እንቅስቃሴም ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት እየተገለጸ ይገኛል፡፡
  • 22holy-synod-2004-ginbot-annual-meeting-decision-on-mahibere-kidusan 221

 

የዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ ድጋፍ ድርጅት ኖርዌይ አንድነትና ሰማያዊ ፓርቲ የሚያደርጉትን ሰላማዊ ትግል እንደሚደግፍ አጋርነቱን አሳያ

$
0
0

May 1/2014

በዛሬው ቀን በኖርዌይ በተከበረው አለም አቀፍ የሰራተኞች ቀን ላይ በመገኛት የዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ ድጋፍ ድርጅት ኖርዌይ አንድነትና ሰማያዊ ፓርቲ በሀገር ቤት የሚደረገውን ሰላማዊ ትግል እንደሚደግፍ አጋርነቱን አሳያ::
UDJ & Blue  ሜይ 1, አለም አቀፍ የላብ አደሮችና የሰራተኞች ቀን በየአመቱ በመላው አለም በተለያዩ አህጉራት በደማቅ ሁኔታ እንደሚከበር ይታወቃል:: ይህ መከበር ከጀመረ ከመቶ ሃያ አመት በላይ የሆነው የላብ አደሮችና የሰራተኞች ቀን ዘንድሮም ሜይ 1 ቀን 2014 (ሚያዚያ 23 ቀን 2006 ዓ.ም ) በተለያዩ አህጉራት ተከብሮል::   በዛሬውም ቀን ሜይ 1 ቀን 2014 በኦስሎና በኖርዌይ በተለያዩ ከተሞች በደማቃ ሁኔታ የተከበረ ሲሆን የተለያዩ  የፖለቲካ ድርጅቶች፣  በሰብአዊ መብትድርጅቶች፣  ሌሎችም ድርጅቶች እንዲሁም በኖርዊይ የሚኖሩ የተለያዩ ሀገራት  ማህበረሰብ ክፍሎች (community) የየሀገራቸውን ባንዲራ እና የየድርጅታቸውን አርማ በመያዝ የሰራተኛውን መብት መከበር የሚጠይቁና ሌሎችንም የተለያዩ መፈክሮችን፣ አርማዎችን በመያዝ  በደማቅ ሁኔታ አክብረዋል::   በኦስሎ እና በተለያዩ ከተሞች የሚኖሩ የዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ ድጋፍ ድርጅት ኖርዌይ አባሎች የድጋፍ ድርጅቱ ለአባሎቹ ባደረገላቸው የሰልፍ ጥሪ መሰረት ተሳታፊ የሆኑ ሲሆን በዚሁ በኢትዮጵያ ሕዝብ ላይ የሚደርሰውን የሰብዊ መብት እረገጣ የተቃወሙ ሲሆን ለአንድነት እና ሰማያዊ ፓርቲ ያላቸውንም ድጋፍ አሳይተዋል:: በአሁኑ ሰአት የወያኔ መንግስት በኢትዮጵያሕዝብ ላይ እያደረሰ ያለውን የሰበሃዊ መብት እረገጣ ፣አፈና፣ እስራትና ግድያ በመቃወም አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) እና ሰማያዊ ፓርቲ ሰለማዊ ትግል እያደረጉ እንዳለና በሰላማዊ ትግል የወያኔን መንግስት እየተፋለሙት እንደሆነ ይታወቃል:: የዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ ድጋፍ ድርጅት ኖርዌይ አባሎችና አመራሮች የተለያዩ መፈክሮችን በመያዝ እና በማሰማት ለአንድነት እና ሰማያዊ ፓርቲ ያላቸውን የድጋፍ አጋርነታቸውን በማሳየት በደማቅ ሁኔታ አክብረዋል:: ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ !!! ዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ ድጋፍ ድርጅት ኖርዌይ

ጭፍጨፋውና አፈናው ይቁም፤ ወያኔ ይወገድ !!!

$
0
0

ginbot 7ግንቦት 7: የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲንቅናቄ፣ ዘረኛው ወያኔ በኦሮሚያ ሕዝብና ወጣቶች ላይ እያካሄደው ያለውን አረመኔያዊ ጭፍጨፋ፣ እስርና አፈናን በጥብቅ ይቃወማል። ህወሓት፣ ኦህዴድ እና በዚህ ጭፍጨፋ እጃቸው ያለበት ሁሉ ከተጠያቂነት የማያመልጡ መሆኑን ያስገነዝባል።

የአሮሚያ ወጣቶች በአዲስ አበባ ማስተር ፕላን ስም የድሀ ገበሬዎች መፈናቀልን መቃወማቸው ፍትሀዊ ነው። የወያኔ “ማስተር ፕላኖች” የወያኔ የዘረፋ እቅዶች መሆናቸው በተደጋጋሚ የታየ ጉዳይ ነው። ነዋሪዎቹን ያላማከረ፣ ግንባር ቀደም ባለጉዳዮችን ባለቤት ያላደረገ፣ የሕዝብ ይሁንታ ያላገኘ ማስተር ፕላን ተፈፃሚ ማድረግ አይቻልም።

ወያኔ ኦሮሚያን ብቻ ሳይሆን መላዋን ኢትዮጵያ በምስለኔዎቹ አማካይነት እየገዛ የኢትዮጵያን ውድ ልጆች በራሳቸው ጉዳይ ባይተዋር አድርጓቸዋል። ኦህዴድ በወያኔ ቅጥረኛነት የኦሮሚያ ወጣቶችን በማስጨፍጨፍ ላይ ያለ እኩይ የአድርባዮች ስብስብ ነው።  ወጣቶች የተቃወሙት ይህንን ነው።እነዚህ ወጣቶች በአካባቢያቸው ጉዳይ ብቻ ሳይሆን በመላው ኢትዮጵያ ጉዳይ ያገባቸዋል። ድምፃቸው ሊሰማ ይገባል። የሌላው አካባቢም ወጣት የኦሮሚያ ገበሬ መፈናቀል ያገባዋል። ኢትዮጵያዊያን በኢትዮጵያ ውስጥ በሚደረግ ጉዳይ ሁሉ ያገባናል። በየትኛውም የኢትዮጵያ ክልል ውስጥ ወያኔ የራሱን እቅድ እንዲጭንብን አንፈልግም።

ግንቦት 7: የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ፣ መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ፣ የኦሮሞ ወጣቶች ጥያቄ የመላው ኢትዮጵያ ሕዝብ ጥያቄ አድርጎ እንዲወስድ ጥሪ ያደርጋል።  በጉራፈርዳና በቤንሻንጉል የተጀመረው መፈናቀል ዛሬ አዲስ አበባ አጎራባች ከተሞች ደርሷል። በአምቦ ይህንን የተቃወሙ ወጣቶች በግፍ ተጨፍጭፈዋል፤ በሌሎች ቦታዎችም ላይ ግድያውና እስሩ በርትቷል። ወጣቱ  የጥይት እራት ሆኖ እስኪያልቅ መጠበቅ አንችልም፤ ሁሉም ትግሉን ይቀላቀል።

የወያኔ የጥቃት ሰለባ የሆኑት የአዲስ አበባ ማስተር ፕላን ጉዳይን ያነሱ ወጣቶች ብቻ  አይደሉም። በአንድ ወይም በሌላ መንገድ የወያኔን አምባገንነት የተቃወሙ በሙሉ የጥቃቱ ሰላባዎች ናቸው። ለሰልፍ ቅስቀሳ አደረጋችሁ በሚል የታሰሩ የሰማያዊ ፓርቲ ወጣቶች ሰልፉ ተደርጎ  ካለቀ በኋላም አልተፈቱም።  ይህ ሰቆቃ ማብቃት አለበት።

ጭፍጨፋውና አፈናው ይቁም፤ ወያኔ ይወገድ !!!

ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ !!!

ሰበር ዜና፦ በአሮማያ ዩኒቨርሲቲ በፈነዳ ፈንጂ ሰባ ሰዎች ተጎዱ

$
0
0

በሃረር አሮማያ ዪኒቨርሲቲ ማንነታቸው ባልታወቁ ሰዎች በፈነዳ ፈንጂ እግር ኳስ በማየት ላይ በነበሩ ሰባ ተማሪዎች ላይ ጉዳት መድረሱንና አንድ ሰው መሞቱን የኢትዮጵያ ፌዴራል ፖሊስ አስታወቀ።

Breking Newsዝርዝሩን ይዘን እንመለሳለን

በአንድነት ፓርቲ ቅስቀሳ – ቪዲዮ ይዘናል


አንድነት ፓርቲ ሚያዝያ 26 ቀን 2006 ዓ.ም በአዲስ አበባ “የእሪታ ቀን” በሚል ለሚያካሂደው ሰላማዊ ሰልፍ ይቀላቀሉ! (ግዛቸው ሽፈራው የአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ሊቀመንበር)

$
0
0

ጤና ይስጥልኝ !

 

ግዛቸው ሽፈራው እባላለሁ። የአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) ሊቀመንበር ነኝ።  አንድነት በኢትዮጵያ ሕጋዊ ፍቃድ አግኘቶ፣ በአገሪቷ ባሉ ክልሎች ሁሉ ሰላማዊ በሆነ መንገድ የሚንቀሳቀሰ ድርጅት ነው። አንድነት ከማንም ግለሰብና ድርጅት ጋር ፀብ የለዉም። የአንድነት ፖለቲካ የኢትዮጵያዊነት፣ የፍቅርና የመቻቻል ፖለቲካ ነው።  አላማችን ፣ የበለፀገች፣ ልጆቿ፣ በዘር ፣ በሃይማኖት፣ በጾታ ልዩነት ሳይደርገባቸው እኩል የሆኑባት፣ አንድነቷና ሉዓላዊነቷ የተጠበቀ ኢትዮጵያን መመስረት ነው።

GizachewShiferaw

ግዛቸው ሽፈራው , የአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) ሊቀመንበር

 

አሁን በስልጣን ላይ ያለው የኢሕአዴግ መራሹ መንግስት፣  ግልጽነት የጎድለው፣ ተጠያቂነት የሌለው፣ በሙስና የተዘፈቀና የመልካም አስተዳደር ችግር ያለበት እንደመሆኑ፣  በሕዝብ ላይ ትልቅ በደል እያደረሰ ይገኛል። የሚከተለው የተሳሳተና ጎጂ የመሬት ፖሊሲ፣  ዜጎች፣ በልማት ስም፣ በቂ ካሳ ሳይከፈላቸው፣ ከቤታቸው እና ከእርሻ ቦታቸው በኃይል እንዲፈናቀሉ እያደረገ ነው። የሰብአዊ መብት ረገጣው፣ ተማሪዎች፣ ጋዜጠኞች የፖለቲካ ፓርቲ አባላት ….. በግፍ መታሰራቸው፣ የኑሮ ዉድነቱ ሕዝቡ ከሚሸከመው በላይ እየሆነበት ነው።

 

ሕዝባችን ከዚህ የተሻለ ይገባዋል።  ኢትዮጵያዉያን አሁን ያለውን አሳዛኝ ሁኔታ አንቀበለም በማለት፣ ለዉጥ መጠየቅ፣  ባለስልጣናትን ተጠያቂ ማድረግ ይኖርብናል።

 

ሕዝቡ ድምጹን ማሰማት የሚችልበት መድረክ ያገኝ ዘንድ፣ አንድነት፣ በሚመለከታቸው የመንግስት አካላት እውቅና ያገኘበት፣ ሁለት ታላላቅ ሰላማዊ ሰልፎችን ፣ እሑድ ሚያዚያ 26 ቀን፣ በአዲስ አበባ እና በደቡክ ክልል በምትገኝ የድራሼ/ጊዶሌ አዘጋጅቷል። የአዲስ አበባ እና የጊዶሌ ነዋሪዎች፣ በነቂስ ወጥተው ድምጻቸውን እንዲያሰሙ በአክብሮት ጥሪ አቀርባለሁ።

 

ነጻነት ነጻ አይደለም። ነጻነትን ከሌሎች አናገኝም። ነጻነትን እኛዉ እራሳችን ነን ለራሳችን ማወጅ የምንችለው። እራሳችንን በግል ካያነው፣ ምንም ማድረግ የማንችል፣  አንድ ተራ ሰው አድርገን ልንቆጠር እንችላለን። ነገር ግን ተራ ሰዎች፣  በሚሊዮን ሲቆጠሩ፣ እነርሱን ማነቃነቅ የሚችል ምንም ኃይል አይኖርም። እንነሳ። ሰልፍ እንዉጣ። ድምጻችንን እናሰማ። ከሚሊዮኖች አንዱ እንሁን ! እራሳችንን ነጻ በማወጣት አገራችንን ነጻ እናውጣ !

 

እንግዚአብሄር አገራችን ኢትዮጵያን ይባርካት

 

ግዛቸው ሽፈራዉ

 

 

 

 

ካዛንቺስ በሚገኘው ፖሊስ ጣቢያ የታሰሩት የአንድነት አመራሮችና ጋዜጠኛ ፍ/ቤት ቀርበው የ11 ቀን ቀጠሮ ተጠየቀባቸው፡፡

$
0
0

Neb34የአንድነት ፓርቲ ሥራ አስፈፃሚና የአዲስ አበባ ሰብሳቢ አቶ ዘካርያስ የማነብርሃን ፣አቶ ዘላለም ደበበ የአንድነት ፓርቲ የህዝብ ግንኙነት ቋሚ ኮሚቴ አባል እና የፍኖተ ነፃነት ዋና አዘጋጅ ጋዜጠኛ ነብዩ ኃይሉ እንዲሁም የመኪናው ሹፌር ነፃነት ዘገየ ሜክሲኮ በሚገኘው የመጀመሪያ ደረጃ ፍ/ቤት ዛሬ ቀርበው ሰላማዊ ሰልፍ እንጂ ለመኪና ቅስቀሳ አልተፈቀደም ፤ ቅስቀሳውን የደረጉት የተከለከለ ቦታ ነው ድርጊቱም ያደረጉት ሆነ ብለው ብጥብጥና ሁከት ለማስነሳት ነው፣ የዋስትና ቢሰጣቸው ከግብረአበሮቻቸው ጋር በመሆን ሁከት ያስነሳሉ በማለት የዋስትና መብታቸውን ተከልክለው የ11 ቀን የጊዜ ቀጠሮ ተጠይቆባቸዋል፡፡

ኢቲቪ የአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) እሁድ የሚያደርገውን ሰላማዊ ሰልፍ ማስታወቂያ አላስተናግድም አለ፡፡

$
0
0
የአንድነት ፓርቲ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ሀብታሙ አያሌው

የአንድነት ፓርቲ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ሀብታሙ አያሌው

አንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) እሁድ ሚያዝያ 26 ቀን 2006 ዓ.ም ለሚያደርገው ሰላማዊ ሰልፍ የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ድርጅት አላስተናግድም ማለቱን የአንድነት ፓርቲ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ሀብታሙ አያሌው ገለጹ፡፡ የህ/ግ ኃላፊው እንደገለጹት ከሆነ ማንኛውንም ህጋዊ አካል ወይንም ዜጋ በእኩልነት ማስተናገድ የሚገባው የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ምንም አይነት ህጋዊ ምክንያት ሳያቀርብ አናስተናግድም ማለቱ አንድ የሕዝብ አገልጋይ ነኝ ከሚል ተቋም የማይጠበቅ እና ተቋሙ በእርግጥም የህዝብ አገልጋይ አለመሆኑን በድጋሚ በተግባር ያረጋገጠበት ነው ሲሉ ገልጸዋል፡፡ እንደ ህዝብ ግንኙነቱ ገለፃ ፓርቲው ጉዳዩን በቸልታ እንደማያየው እና ወደ ፍርድ ቤት እንደሚወስደውም ታውቋል፡፡ የኢትዮጵያ ቴሌቪዢን የማስታወቂያ ክፍል ኃላፊ አቶ ሰይፉ አለምሰገድና ወ/ት ሸዋዬ የማስታወቂያ ክፍል ኤክስፐርት በእጅ ስልካቸው ደውለን ምላሽ ለመስጠት ፈቃደኛ ባለመሆናቸው የነሱን ሀሳብ ልናካትት አልቻልንም፡፡

 

 

 

etv

የኢትዮጵያ ጋዜጠኞች መድረክ (ኢጋመ) ፕሬዝደንት ጋዜጠኛ በትረ ያቆብ ተሰደደ

$
0
0

betre yacobከሳምንት በፊት የኢትዮጵያ ጋዜጠኞች መድረክ ፕሬዝዳንትና ምክትል ፕሬዝዳንት በአፍሪካ ህብረት ጋባዥነት የኢትዮጵያን ችግርና አፈና በተለይ ላይ ሚዲያው ላይ ያለውን ጫና እና ጋዜጠኞች ላይ የሚደርሰውን አፈና ለመግለጽ ወደ አንጎላ አቅንተው ነበር፡፡ በጉዳዩ ሰፊ ማብራሪያ የሰጡ ሲሆን ለአፍሪካ ህብረትም የመፍትሄ ሀሳብ ማቅረቡና ለሰብአዊ መብት ኮሚሽነሩም መልስ መስጠቱ ይታወቃል፡፡

ጋዜጠኛ በትረ ያቆብ ስብሰባው ከተጠናቀቀ በኋላ ወደ አገሩ ለመመለስ በሚዘጋጅበት ወቅት የዓለም አቀፍ የጋዜጠኛ ማህበራትን ጨምሮ ሌሎች የዓለም አቀፍ ተቋማት ሳይቀሩ እሱን ለማሰር የተደረገው ዝግጅት በተጨባጭ ማስረጃ ስላቀረቡለት መሰደዱን የነገረ ኢትዮጵያ ምንጮች ገልጸዋል፡፡ የዞን ዘጠኝ ጦማሪዎች በታሰሩበት ወቅት ፖሊስ የበትረ ያቆብን ቤት በመፈተሸ ያገኘውን ወረቀት ሁሉ እንደወሰደም ምንጮቻችን ጨምረው ገልጸዋል፡፡

ጋዜጠኛ በትረ ያቆብ አንጎላ በተደረገው የአፍሪካ ህብረት ስብሰባ ኮሚሽነሩን በግል እንዳገኛቸውና ኮሚሽነሩም በቅርቡ ወደ ኢትዮጵያ እንደሚመጡ በመግለጽ እንዲሚያገኙት ቃል ገብተውለት እንደነበር ተገልጻል፡፡ በተጨማም ከበርካታ የአፍሪካ ህብረት ባለስልጣናት ጋር ስለ ኢትዮጵያ ወቅታዊ ሁኔታና በሚዲያው ላይ ስለሚደረገው ጫና የተወያዩ ሲሆን አብዛኛዎቹ በተለያዩ መንገዶች እገዛ ለማድረግ ቃል ገብተውለት እንደነበር ከታማኝ ምንጮች ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡ በስብሰባው ወቅት ኢትዮጵያንና የኢትዮጵያ ጋዜጠኞች መድረክን ወቅታዊ ሁኔታ የሚገልጹ ጽሁፎች ለተሰብሰብሳቢዎቹ ተበትነዋል፡፡

የኢትዮጵያ ጋዜጠኞች መድረክ መቋቋም ያስፈራቸው ሌሎች የጋዜጠኞች ማህበራት በትረ ያቆብን ለሂውማን ራይትስ ዎች፣ ለሲፒጄ፣ ለአርቲክል 19ና ሌሎች የጋዜጠኞች ማህበራት ይሰራል፣ ይሰልላል፣ የእነዚህ ድርጅቶች ተላላኪ ነው፣ ሪፖርት ይጽፋል በሚል በመግለጫቸውና ‹‹የጋዜጠኞች ክብ ጠረጴዛ›› በተባለው ፕሮግራም ይከሱት እንደነበር ጋዜጠኛ በትረ ያቆብ አገር ውስጥ በነበረበት ወቅት ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጻል፡፡

ምንጭ፡- ነገረ ኢትዮጵያ

የአዲስ-ኦሮምያ ጉዳይ በመቐለ-እንደርታ ዓይን –ከአብርሃ ደስታ

$
0
0

Wallaggaa2014_3

ስለ አዲስ አበባ ማስተር ፕላንና የኦሮምያ አርሶአደሮች መፈናቀል ጉዳይ በፃፍኩት ላይ “የኦሮሞ ተማሪዎች ዓመፅ ከብሄር አንፃር አትየው፤ መታየት ካለበት አርሶአደሮቹ ከቀያቸው ካለመፈናቀል መብት አንፃር ነው” የሚል አስተያየት ደርሶኛል። እኔም ይሄን ጉዳይ በቅርበት ከማውቀው የመቐለ እንደርታ አርሶአደሮች ልምድ አንፃር ልየው ይፈቀድልኝ።

በመቐለ የከተማ ዕድገት ፕላን መሰረት አንዳንድ በከተማው ዙርያ የሚገኙ የገጠር መንደሮች ወደ መቐለ ከተማ ይገባሉ። ይህንን ዉሳኔ ባከባቢው አርሶአደሮች ከፍተኛ ተቃውሞ አጋጥሞታል። አርሶአደሮች የተቃውሞ ሰልፍ ለማካሄድ ሞክረዋል። የክልል ፖሊስ፣ የፌደራል ፖሊስ እንዲሁም የመከላከያ ሰራዊት አባላት ጣልቃ ገብተው የኃይል እርምጃ ወስደው ሰልፈኞቹን ደብድበው፣ አስረው፣ ገድለው ዓመፁ ለግዜው አስቁመውታል። ጥያቄው ግን እስካሁን ድረስ አለ። በዚህ ምክንያት ያከባቢው አርሶአደሮች የመንግስት አገልግሎት ተነፍገዋል። አርሶአደሮቹም ከመንግስት ጋር ላለመተባበር አድመዋል። ለምሳሌ የእግሪሐሪባ አርሶአደሮች ልጆች የመማር መብታቸው ተነፍጓል። የነዚህ አርሶአደሮች ልጆች ለምን እንዳይማሩ ተከለከሉ? ወላጆቻቸው መሬታቸው ወደ ከተማ መግባቱ በመቃወማቸው ምክንያት ነው። የትግራይ ክልል ባለስልጣናት “የወላጆቻቹ መሬት የከተማ እንዲሆን ካልፈቀዱ እናንተ ህፃናት እዚሁ ትምህርትቤት አትማሩም። ምክንያቱም ይሄ ትምህርትቤት የከተማ ሆኗል” አሏቸው። እናም እስካሁን ድረስ እነኚህ ልጆች የመማር መብታቸው እንደተነፈጉ ነው።

“የገጠር መሬት ወደ ከተማ ሲገባ ለምን ይህን ያህል ተቃውሞ ይነሳበታል?” የሚል ጥያቄ መነሳቱ ተገቢ ነው። ከተማ ማደግ አለበት። ከተማ ሲያድግ በዙርያው ወዳለ የገጠር መንደር ይሰፋል። ግን ለምን አርሶአደሮች አምርረው ይቃወሙታል?

(አንደኛ) አርሶአደሮች ከቀያቸው መፈናቀል አይፈልጉም። ለመሬታቸው ልዩ ፍቅር አላቸው። የያለ መፈናቀል መብትም አላቸው (በመርህ ደረጃ)። አንድን አርሶአደር ያለፍቃዱ ከቀዩ መፈናቀል የለበትም። ግን መንግስት በኃይል ያፈናቅላቸዋል። መንግስት በአንድ በኩል “አርሶአደሮች መሬት ከተሰጣቸው ሽጠው ከቀያቸው ይፈናቀላሉ፣ ስለዚህ መሬት ሊሰጣቸው አይገባም” በሚል ስሌት መሬት የመንግስት አድርጎታል። በኢትዮጵያ ታሪክ አርሶአደሮች ከቀያቸው የሚፈናቀሉ በኃይል እንጂ በፍቃዳቸው አይደለም። በዘመነ መሳፍንት ግዜ አርሶአደሮች መሬት አልባ ጭሰኛ የሆኑ በኃይል እንጂ በፍቃዳቸው አልነበረም። አሁንም በመንግስት ትእዛዝ እንጂ በፍላጎቱ ከቀዩ የሚፈናቀል የለም። ስለዚህ ተቃውሞው ከቀያቸው ላለመፈናቀል የሚያደርጉት ትግል ነው።

ግን አርሶአድሮች ከቀያቸው ያለመፈናቀል መብት ካላቸው ለምን ወደ ተቃውሞና ዓመፅ ይሄዳሉ? አርሶአደሮች መፈናቀል አይፈልጉም። መንግስት በኃይል ከቀያቸው እንዲፈናቀሉ ያስገድዳቸዋል። መንግስት እንዲፈናቀሉ ሲያስገድዳቸው ለምን አቤት አይሉም? አቤት ለማለት’ኮ ገለልተኛ የፍትሕ አካላት መኖር አለባቸው። የፍትሕ አካላት ሲኖሩ ደግሞ የያለመፈናቀል መብት በሕግ የተደነገገ መሆን አለበት። ከመሬት የያለመፈናቀል መብት በሕግ የተደነገገ እንዲሆን መሬት የዜጎች መሆን አለበት።
mekele
አሁን በኢህአዴግ ሕገመንግስት መሰረት ዜጎች መሬት ተከራይተው የመጠቀም መብት እንጂ የመሬት ባለቤት የመሆን መብት የላቸውም። መሬት የዜጎች ሳይሆን የመንግስት ነው። ስለዚህ ዜጎች መሬት የመከራየት (ሊዝ የመሬት ኪራይ መሆኑ ነው) መብት አላቸው። ባለቤትነቱ ግን የመንግስት ነው። ስለዚህ አንድ ተካራይ ከተከራየሁት ቤት (መሬት) መልቀቅ (መነሳት) የለብኝም ብሎ መከራከር አይችልም። ተግባሩ ግን መቃወም ይችላል።

እናም አርሶአደሮቹ ከመሬታችን አንፈናቀልም ሲሉ መሬትኮ የመንግስት እንጂ የናንተ አይደለም፤ ስለዚህ ትነሳላቹ ይሏቸዋል። አርሶአደሮቹም “መሬትኮ የመንግስት መሆን የለበትም” ሲሉ “መሬት የመንግስት ካልሆነማ መሬታችሁን ሽጣቹ መሬት አልባ ትሆናላቹ። መሬት በጥቂት ሃብታሞች እጅ ይገባል” የሚል መልስ ይሰጣቸዋል። መሬታቹ ሌሎች ሊወስዱት ስለሚችሉ ቀድመን እኛ ወስደነዋል ዓይነት ማለት ነው።

ስለዚህ አርሶአደሮቹ መሬታችን አንሰጥም ብለው በሕግ ፊት እንዳይከራከሩ ሕጉ አይደግፋቸውም። ምክንያቱም ሕጉ መሬት ለዜጎች ሳይሆን ለመንግስት ነው የሰጠው። ስለዚህ የሕግ ድጋፍ የላቸውም። የህግ ድጋፍ ባይኖራቸው እንኳ ተግባሩ ትክክል አለመሆኑ ያውቃሉ። እናም ይቃወሙታል። መቃወም ሳይፈቀድላቸው ሲቀር ያምፃሉ። ሲያምፁ በኃይል ይደፈጠጣሉ። እናም አማራጭ ስለሌላቸው አኩርፈው ይቀመጣሉ። በኦሮምያ ግን ዓመፁን አቀጣጠሉት።

ስለዚህ የችግሩ መንስኤ የመንግስት የተሳሳተ የመሬት ፖሊሲ ነው። መሬት የህዝብ (የዜጎች) ቢሆን ኑሮ አርሶአድሮች ከመሬታቸው ያለመፈናቀል መብታቸው በሕግ ይከበርላቸው ነበር (ገለልተኛ የዳኝነት ስርዓት ሲኖር ማለት ነው)። ምክንያቱም መሬት የአርሶአደሮች ከሆነ ማንም ከቀያቸው እንዲፈናቀሉ አያስገድዳቸውም ነበር። መሬት ለራሹ ከተሰጠ አርሶአደሮች ያለ ፍቃዳቸው ከመሬታቸው (ከቀያቸው) አይፈናቀሉም። ካልተፈናቀሉ ደግሞ መሬታችን ወደ ከተማ ይገባል ብለው ዓመፅ አይቀሰቅሱም ነበር። ስለዚህ የችግሩ ምክንያት የመሬት ፖሊሲው ነው።

(ሁለት) አስፈላጊ ሁኖ ሲገኝ አርሶአደሮች የሚፈናቀሉበት ሁኔታ ሊፈጠር ይችላል። ይሄ የሚሆነው ግን አርሶአደሮችን በማሳመን (በፍቃዳቸው) ሁኖ ለመሬታቸው ተገቢ ካሳ (ራሳቸው በጠየቁት መሰረት) ሊከፈላቸው ይገባል። በመቐለ ዙርያ ያሉ አርሶአደሮች ግን ከመሬታቸው ተፈናቅለው ሲያበቁ በቂ ካሳም አይሰጣቸውም። የካሳ መጠን የሚወስነው መንግስት ነው (ካሳ የማያገኙም አሉ)። መሬታቸው አጥተው በቂ ካሳ ካላገኙ ከዚህ የባሰ መነቀል አለንዴ? ይህ ሲሆን እንዴት አይቃወሙም? የኦሮምያ ጉዳይም ተመሳሳይ ስጋት ሊጭር ይችላል።

(ሦስት) “መሬታቹ የከተማ አካል ሁኗል” በሚል ምክንያት አርሶአድሮች ከቀያቸው ያለፍቃዳቸውና ያለ በቂ ካሳ ከተፈናቀሉ በኋላ መሬቱ በሙስና ለሙሰኞች ይቸበቸባል። መሬት የመንግስት በመሆኑ እንዲሁም መንግስትና ገዥው ፓርቲ በመቀላቀላቸው ምክንያት የገዥው ፓርቲ ጥቂት ካድሬዎች መንግስት ሁነዋልና ከአርሶአደሮች የተረከቡትን መሬት እንደፈለጉ ለፈለጉትን ባለሃብት ይሸጡታል። መሬት ከአርሶአደሮች ነጥቀው ለራሳቸው ያደርጉታል። ወይ ይሸጡታል ወይም ደግሞ ህንፃ ያቆሙለታል። መሬት አይሸጥም አይለወጥም እየተባለ የመንግስት አካላት ግን እንደፈለጉ ይሸጡታል፣ ይለውጡታል። መሬት እንዳይሸጥ እንዳይለውጥ የተከለከለ አርሶአደሮቹ እንጂ መንግስትማ የፈለገ ያደርጋል። እናም ከአርሶአደሮች የተነጠቀ መሬት ለግል ሃብታሞች እየተሸጠ እየተመለከቱ እንዴት አይቃወሙም? እንዴት ለመሬታቸው አያምፁም? በኦሮምያም በእንደርታ የተተገበረውን እንደማይደረግ ምን ማረጋገጫ አለን?
ስለዚህ የመቐለ እንደርታ አጀንዳ በመውሰድ የአዲስ አበባ ኦሮምያ ጉዳይ መገመት ይቻላል። ጉዳዩ ከመንግስት የመሬት ፖሊሲ ጋር ይገናኛል።

“የኦሮምያ ተቃውሞ ፖለቲካዊ አጀንዳ አለው” ካላችሁኝም ያው ፖለቲካዊ ተልእኮ ሊኖረው ይችላል። ፖለቲካዊ ተልእኮ ያለው ዓመፅ ሲቀሰቀስምኮ ያለው ፖለቲካዊ ሁኔታ መሰረት አድርጎ ነው። ፖለቲካዊ ዓመፅ የሚቀሰቀሰው ጭቆና ሲኖር ነው። የፍትሕ እጦት ሲኖር ነው። የዴሞክራሲ እጦት ሲኖር ነው። ነፃነት ሲታፈን ነው። ስለዚህ ዓመፁ ፖለቲካዊ አጀንዳ ያለው ከሆነም ያው መንስኤው ደግሞ የኢህአዴግ ጨቋኝ አገዛዝ መሆኑ ነው። ምክንያቱም በሀገሪቱ ፍትሕ ቢሰፍን ኑሮ ዜጎች ፖለቲካዊ አጀንዳ ይዘው አያምፁም ነበርና ነው።
የፖለቲካዊ ዓመፅ መንስኤ ጭቆና ቢሆንም ዓመፅ ግን የጭቆና ነፀብራቅ እንጂ ጭቆና የሚወገድበት ትክክለኛ ስትራተጂ አይደለም። በዓመፅ ጨቋኞችን ከስልጣን ማባረር ይቻል ይሆናል። በዓመፅ ጭቆናን ማስወገድ ግን አይቻልም። ጭቆና የሚወገደው ዴሞክራሲ በማስፈን ነው። በዓመፅ የሚገነባ ዴሞክራሲ ደግሞ የለም። የዴሞክራሲ መንገድ ዴሞክራሲ ነው። ዓመፅ የሰው ህይወትና ንብረት ይበላል። በዓመፁ ምክንያት ህይወታቸው ላጡ ተማሪዎች ጥልቅ ሐዘን ይሰማኛል።

Viewing all 15006 articles
Browse latest View live