Quantcast
Channel: Ethiopian News | ዘ-ሐበሻ | Latest News Provider | News For All
Viewing all 15006 articles
Browse latest View live

Hiber Radio: ኢትዮጵያ ከሰሜን ኮሪያ በምስጢር መሳሪያ መግዛቱዋ ተሰማ

0
0
የህብር ሬዲዮ ሚያዚያ 12  ቀን 2006 ፕሮግራም
ጋዜጠኛ ሃብታሙ አሰፋ

ጋዜጠኛ ሃብታሙ አሰፋ

<<…ኢትዮጵያውያን የፋሲካን በዓል በውጭ አገር ስናከብር በአገር ቤት በዓሉን በደስታ ለማሳለፍ ያልቻሉ ኑሮው የከበዳቸው እንዳሉ መርሳት የለብንም…>>

ብዑዕ አቡነ ዮሴፍ የኔቫዳ፣የአሪዞናና ዩታ አገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ለህብር ሬዲዮ ከሰጡት ማብራሪያ (ሙሉውን ያዳምጡ)

ላሊበላ በውጭ ጎብኒ እይታ  

ኦቲዝም ምንድነው? እውን ልጆቻችንን አውቀን በጊዜ ተገቢውን ቴራፒ እንዲወስዱ እናደርጋለን?

በኦቲዝም ውስጥ ያሉ ልጆች ያሏቸው ልጆች ወላጆች ምን ይላሉ?

ሰናይት አድማሱ የስነ ልቦና ባለሙያ እና  

ወ/ሮ ፌበን ፋንቱ ወላጅ ከሎስ አንጀለስ ማብራሪያ ሰጥተውናል (ክፍል ሁለት ሙሉውን ያዳምጡ)

 የጋዜጠኛ ነብዩ ሲራክ ማስታወሻ ከሳውዲ እስር ቤት  

ሌሎችም ዝግጅቶች

ዜናዎቻችን

የኬንያ መንግስት 65 ኢትዮጵያውያን ስደተኞች በአልሸባብ ስም አሰረ

በሳውዲ 3ሺህ ኢትዮጵያውያን የሚማሩበት ት/ቤት በቆንስላው ቸልተኝነት የመማር ማስተማሩ ሂደት እየተስተጓጎለ ነው

መምህራን የስራ ማቆም አድማ አድርገዋል

ግብጽ ለደቡብ ሱዳን በራሷ ወጭ ግድብ ልስራ አለች

ኢትዮጵያ ከሰሜን ኮሪያ በምስጢር መሳሪያ መግዛቱዋ ተሰማ

በአገር ቤት የዘንድሮም የበዓል ገበያ የዋጋ ንረት የታየበት ነበር

ኢትዮጵያዊቷን የሆቴል አስተናጋጅ ለመድፈር የሞከረ የሳውዲ ዜጋ በነጻ ተለቀቀ

ሌሎችም ዜናዎች አሉ


[የፋሲካ ወግ] ቴሌፎኑ ‘ለግዜው’ጥሪ አይቀበልም –ክንፉ አሰፋ (ጋዜጠኛ)

0
0

ክንፉ አሰፋ

“የደወሉላቸው ደምበኛ ለግዜው ጥሪ አይቀበሉም።…” የምትለዋ አሰልቺ የቴሌ መልእክት ያላጋጠመው ቢኖር ወደ ኢትዮጵያ ስልክ ደውሎ የማያውቅ ሰው ብቻ መሆን አለበት። ኮ/ል መንግስቱ ሃይለማርያም ወደ ቀድሞ ወዳጆቻቸው መደዋወል ጀመሩና በመሃል ተስፋ ቆረጡ አሉ። አስር ለሚያህሉ አርሶአደሮች እና የሰራዊቱ አባላት ዘንድ ደውለው አልተሳካለቸውም። ለሁሉም ጥሪ ያገኙት ምላሽ “የደወሉላቸው ደምበኛ ለግዜው ጥሪ አይቀበሉም።” የሚል ሲሆንባቸው ራሳቸውን ነቀነቁ። ሰው ሁሉ የጨከነባቸው መሰላቸው። እንዲህም አሉ። “የሃገሬ ሰው እንኳን የስልክ ጥሪ፤ የእናት ሃገር ጥሪስ መች ተቀበለ።”

ለአመታት በተከታታይ በሁለት ድጅት እያደገች ያለች ሃገር የስልክ መስመር ችግር ይገጥማታል ብሎ ማሰብ ይከብዳል። ችግሩን በደንብ ላልተረዳው፣ ሰው የሞባይል ስልክ የሚገዛው እንዲሁ ይዞ ለመታየት ነው ያስብል ይሆናል። ይህ አባባል በከፊል ትክክል ነው። ዘመናዊ ስልክ በመያዝ ለላንቲካነት ብቻ የሚጠቀሙበት ሰዎች አይጠፉም። የቻይናው ቀፎ ከሞዴል አርሶ አደሮች አልፎ ተራው አርሶ-አደር እጅ ላይም ገብቷል። አብዛኞቹ ግን ተንቀሳቃሽ ስልካቸውን አይጠቀሙበትም። ለዚህም ይመስላል በርካታ ተንቀሳቃሽ ስልክ የሚይዙ ሰዎች እንዲሁ ለእይታ እና ለላንቲካ ብቻ የሚመስላቸው። አገልግሎቱን በተመለከተ ግን 99 በመቶ የሚሆነው ችግር የመዋቅር ችግር ነው።

ለዓውዳመቱ ወደ ኢትዮጵያ ስልክ የደወላችሁ ካላችሁ፤ ይህ ነገር እንደገጠማችሁ እርግጥ ነው። ዘንድሮ ደግሞ ቴሌ ከፍቷል። የሞባይሉ መስመርማ እንደ አይን እልም ብሎ ነው የጠፋው። ከበርካታ ሙከራ በኋላ መስመር ያገኘ ሰው ካለ በደስታ ይዘልላል። የተቀባዩም ስልክ ካቃጨለ ተዓምር ነው የሚባለው። ከርማ ብቅ እንደምትለው የአዲስ አበባ መብራት… ልክ እንደ ቧንቧ ውሃ፤ ስልኳም “መጣች – መጣች!” ብሎ መጨፈሩ አይቀርም።

 (በመከራ መስመር ሲገኝ እንዲህ ያስደስታል)

(በመከራ መስመር ሲገኝ እንዲህ ያስደስታል)


“እንኳን አደረሳችሁ!” ለማለት እኔም ወደ ሃገር ቤት ስልክ መታሁ።

“የደወሉላቸው ደምበኛ ለግዜው ጥሪ አይቀበሉም።” የሚል መልስ ነበር ያገኘሁት። ለሁለተኛ ግዜ ስሞክር ደግሞ “የደወሉት ስልክ ለግዜው ከአገልግሎት መስጫ ክልል ውጪ ነው።” የሚል ምላሽ አገኘሁ። ደቂቃ ባልሞላ ግዜ ውስጥ ጥሪ ያማይቀበለው ስልክ ከአገልግሎት መስጫ ክልል መውጣቱ አስገረመኝ። ተስፋ ሳልቆርጥ ደገግሜ ሞከርኩ። ቢያንስ ከአስር ግዜ ሙከራ በኋላ፤ መስመር አገኘሁና ሎተሪ የወጣልኝ ያህል ተሰማኝ።

ደስታዬ ግን ብዙም አልዘለቀም። በመሃል እንግዳ ነገር ተፈጠረ። ስልኩን የተቀበለኝ የደወልኩለት ሰው አልነበረም። የተፈጠረው ክስተት – ባለንበት የመረጃ ዘመን እንደ 17ኛው ክፍለዘመን “ቴሌ በኦፐሬተር መስራት ጀመረ እንዴ?” ያሰኛል። ነገሩ ግን ሌላ ነው። ስልኩን ያነሳው የተለመደው የስልክ ጠላፊ ስለመሆኑ አንዳች ጥርጥር አልነበረኝም። ሶማሌያውያን መርከብ ሲጠልፉ ጸሃዩ መንግስታችን ደግሞ የስልክ ፓይረት መሆኑን ሂዩማን ራይትስ ዎች በዚያን ሰሞን ነግሮን ነበርና።

ውጭ ሃገር ያለ ኢትዮጵያዊ ዘመድ ለመጠየቅ መደወሉ አይቀርም። ተስፋ የማይቆርጥ፤ ደጋግሞ ይሞክራል። እንደ እድል የስልኩን መስመር ካገኘ ደግሞ ሌላ ችግር ይገጥመዋል። ዘው ብለው የሚገቡ የስልክ ጠላፊዎች መስመሩን ያውኩታል። ሌላው አማራጭ ደግሞ አጭር የጽሁፍ መልእክት ነው። በኢትዮጵያ ቴሌኮም አጭር መልእክት ከመላክ ይልቅ ደብዳቤ ጽፎ በፖስታ መላኩ እየፈጠነ መጥቷል። አጭር መልእክት የሚደርሰው ከቀናት ብኋላ ነው። ከላኪው ዘንድ መልዕክቱ መድረሱ ቢረጋገጥም ተቀባዩ ጋ ጨርሶ ላይደርስም ይችላል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ አቶ ሃይለማርያም ደሳለኝ በቅርቡ በሰጡት ጋዤጣዊ መግለጫ “የኢትዮጵያ ቴሌኮም ቴክኖሎጂ ከዴንማርክ፣ ከኖርዌይ እና በከፊል ከእንግሊዝ ቴክኖሎጂ ጋር አንድ ነው” ብለው ነበር። በዚህ መግለጫቸው አቶ ሃይለማርያም የኢትዮጵያን የኢንተርኔት አገልግሎት፣ እንዲሁም የስልክ መስመሩ ጥራት እና አስተማማኝነት በደንብ አድርገው ነበር “ለጋዜጠኞቹ” የገለጹላቸው። ይህን ተናግረው እንዳበቁ ግን የራሳቸውም ስልክ መጠለፉን ሰማን። ጆሮ ለባለቤቱ ባዳ ነው እንዲሉ አልሰሙት ይሆናል እንጂ፤ “እኛ ሲም ካርድ፤ አንተ ደግሞ ቀፎ ነህ!” ይሏቸዋል – ከላይና ከታች ያሉ አለቆቻቸው።

የኢትዮጵያን ስልክ አገልግሎት ከዴንማርክ፣ ኖርዌይ እና እንግሊዝ ጋር አወዳድረው ማወደሳቸው ግን ራሳቸው ካዴሬዎቹንም ሳይቀር ሳያሰፍራቸው አልቀረም። ሰውየው የኢትዮጵያን ቴሌኮም እያወዳደሩ ያሉት 99.9 በመቶ ሳያቋርጥ አገልግሎት ከሚሰጠው አራተኛው ጀንሬሽን የምእራቡ ቴክኖሎጂ ጋር ነው። መቼም ሁሉም ይዋሻሉ። ነብሳቸውን ይመርና አቶ መለስ ዜናዊም ይዋሹ ነበር። ለዛ ያለው ውሸት አለ። እጅ፣ እግርና አይን የሌለው ውሸትም አለ። እንዲህ አይነት ያፈጠጠ ውሸት ግን እመራዋለሁ የሚሉትንም ሕዝብ እንደመናቅ ይቆጠራል። እኚህ ሰው የሞራል እሴታቸውን ሁሉ አሽቀንጥረው ሊጥሉት ይችሉ ይሆናል። ምሁራዊ ግብአታቸውንም ለተራ ፖለቲካ ጥቅም ሊያስወግዱት ይችላሉ። እምነታቸውስ እንዲህ አይነቱን ቅጥፈት ይፈቅድላቸው ይሆን?
የቴሌ የኢንተርኔት አገልግሎት የመንግስት አልባዋ ሶማልያን አንድ መቶኛም። ኮሜዲያን ክበበው ገዳ እንደቀልድ የነገረኝ ቁም-ነገር የኢትዮጵያን ኢንተርኔት ፍጥነት በደንብ ይገልጸዋል። ክበበው ሰሜን አሜሪካ የስራ ጉብኝቱ ወቅት ፎቶ ተነስቶ ለቤተሰቡ በኢሜይል ይልካል። የላከው ፎቶ መድረሱን ለማረጋገጥ በነጋታው ወደ አዲስ አበባ ደወለ።
“ፎቶ ደረሰ?”
“አልደረሰም!”
ሌላ ቀን እንደገና ደውሎ የላከው ፎቶ እንዳልደረሰ ተነገረው። ለሶስተኛ ግዜ ደውሎ ኢሜይሉ እንደደረሰ ጠየቀ። አሁንም አልደረሰም ተባለ። እንዲህ እያለ ሳምንት ሞላው።
“በሳምንቱ እኔ ቀድሜ ደረስኩ።” ነበር ያለው ክበበው።
የኢሜይል መልእክቱ መድረሱ ከተረጋገጠ በኋላ – ሌላ ችግር ገጠመው። ኢሜይሉ ሲከፈት ግማሽ አካሉን ነበር የሚያሳየው። ፎቶው እስኪያወርድ (ዳውንሎድ እስኪያደርግ) ደግሞ ግማሽ ቀን መፍጀቱ ግድ ነበር።

ይህንን አገልግሎት ነው አቶ ሃይለማርያም ከምእራቡ አለም አገልግሎት ጥራትና ፍጥነት ጋር እያወዳደሩ የሚነገሩን። በአስር ሜትር ርቀት ላይ ሆኖ በስልክ መገኛኘት ህልም በሆነበት ሃገር፤ ስለ ስልክ ጥራት መናገር ቅጥፈት ብቻ ሳይሆን የሰውየውንም የሞራል ውድቀት ያመላክታል።
የኢትዮጵያ ቴሌኮም ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ቀጥሎ ትልቅና ግዙፍ የሃገሪቱ ተቋም ነው። እድገቱ ግን ያሳዝናል። በአስር አመት ግዜ ውስጥ ብቻ እንኳን እድገቱ በ75 በመቶ ቁልቁል ወርዷል። ለዚህ ዋናው ምክንያት ተቋሙ አገልግሎት መስጠቱን አቁሞ ወደ ስለላ ተቋም መቀየሩ ነው። ባለፈው ወር ይፋ የሆነው ባለ 100 ገጹ የሂዩማን ራይትስ ዎች ዘገባ ይህንን መንግስታዊ የስልክ እና የኢንተርኔት ጠለፋ አረጋግጧል።

“የተቃዋሚ ፓርቲ አባል የነበረን አንድ ዜጋ አፍነው ካሰሩት በኋላ ውጭ የተደዋወለበትን የስልክ ቁጥር ዝርዝር አሳዩት።” ይላል ጠቀማጭነቱ ዩናይትድ ስቴትስ የሆነው አለም አቀፉ የሰብአዊ መብት ተሟጋች ተቋም። ሰውየው የታሰረው ያልተከፈለ የስልክ ሂሳብ ኖሮበት አልነበረም። ባለስልጣናቱንም አላማም፣ ወይንም መንግስትን በሃይል ለመገልበጥ አላሴረም። ወንጀሉ፤ ከውጭ ሃገር ስልክ ስለተደወለለትና ከወዳጅ ዘመዶቹ ስለተወያየ ብቻ ነበር። ይህ ደግሞ ፍጹም እንግዳ ነገር ነው። ከተለምዶ ልማታዊ መንግስት አስተሳሰብም እጅግ የከፋ!

የዜጎች ሁሉ ስልክ በቴሌ በኩል ይጠለፋል። እንደ ስካይፕ እና ቫይበር ያሉ የቮይስ ኦቨር ስልኮች ደግሞ ፊን ፊሸር በተባለ የኮምፒዩተር ቫይረስ አማካኝነት ይጠለፋሉ። በዚህ አይነት በዜጎች የግል ህይወት ሳይቀር እየገቡ ቴሌን ሙሉ በሙሉ የስለላ ተቋም አደረጉት።

ሞባይል ስልክ እና ኢንተርኔት በአፍሪካ አህጉር በእጅጉ እየተስፋፋ ይገኛል። ጥናቶች እንደሚያሳዩት ከሆነ 30 በመቶ የሚሆነው የአፍሪካ ህዝብ የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ጠጠቃሚ እየሆነ መጥቷል። በኢትዮጵያ ግን የስልክ እና የኢንተርኔት ተጠቃሚው ከ2.5 በመቶ አልዘለቀም።

ጎረቤት የሆነችው የኬንያ ህዝብ 40 በመቶ የዚህ አገልግሎት ተጠቃሚ ነው። መንግስት አልባዋ ሶማልያ እንኳን፣ ስድስት የቴሌፎንና ስልክ አቅራቢ ኩባንያዎች አሏት። የሶማልያ ህዝብ ጥራት ያለው የስልክ መስመር እና ፈጣን የኢንተርኔት አገልግሎት ተጠቃሚ ከሆነ ሰንበትበት ብሏል። በኡጋንዳም የዚህ አገልግሎት ሰጪ በመንግስት ሞኖፖሊ ስር አይደለም። ከሰባት በላይ የግል ኩባንያዎች እየተፎካከሩ ፈጣን አገልግሎት እየሰጡ ጠተቃሚውን ህዝብ ወደ 50 በመቶ አድርሰውታል።

ያለነው በመረጃ ዘመን ነውና ያለመረጃ እና ያለ መረጃ ቴክኖሎጂ እድገት አመጣለሁ ማለት ዘበት ነው የሚሆነው። የኢትዮጵያ ሁኔታ ግን ሃገሪቱን ወደ መረጃ ሳይሆን ወደ ጨለማ ዘመን ነው እየመራት ያለው። እንድምናነበው ከሆነ የኢትዮጵያን ቴሌኮም ለማስፋፋት ከሶስት ቢሊየን ዶላር በላይ ወጪ ሆኗል። ይህ ገንዘብ በትክክል ስራ ላይ ቢውል አባይንም ይገድባል። ለዚህ የእድገት ሳይሆን ይልቁንም የጥፋት ጎዳና ተባባሪ የሆነቸው ቻይናም በውጭ ምንዛሪ እየተከፈላት ቴሌን ብቁ የስለላ ተቋም አድርጋዋለች። የኢኮኖሚ ልማትና ትብብር ሚኒስትሩም ከተለያዩ የኢንዱስትሪ ሃሮች ጋር በመተባበር የቴሌ ጥራት ላይ ሳይሆን የሚሰራው የስለላ ሃርድዌር እና ሶፍትዌር ማስገባቱ ላይ ነው።

የሃገሪቱ ግብር ከፋዮች ገንዘብ መልሶ ራሳቸውን እንዲያፍን መደረጉ እጅግ ያሳዝናል።

የቴሌ መልስ መስጫ ላይ ያለው መልዕክት ግን መሻሻል አለበት። “ለግዜው” የሚለው ቢቀየር ድርጅቱን ከሃሜት ያድነዋል። እናም መልእክቱ እንዲህ ነው መሆን ያለበት፣
“የደወሉላቸው ደምበኛ ‘ለሁልግዜ’ ጥሪ አይቀበሉም። ..”
ከዚያ በኋላ ደዋዩም ተስፋ ቆርጦ መደወል ያቆማል።

ስለፍትህ ሲባል ስርዓቱ ይፍረስ! ፫ (ተመስገን ደሳለኝ)

0
0

Temesgen-Desalegn4ተመስገን ደሳለኝ)

ልዕለ ኃያሏ ሀገረ-አሜሪካን ዛሬ ለተጎናፀፈችው የሕግ የበላይነት የተከበረበት ሥርዓት መሰረት
የጣሉት እነ ቶማስ ጃፈርሰን በነፃነት አዋጃቸው ላይ ‹‹ሁሉም ሰዎች በእኩልነት የተፈጠሩ ናቸው›› በማለት
ሲደነግጉ፤ እንግሊዛዊው ደራሲ ጆርጅ ኦርዌል ደግሞ “Animal Farm” በሚለው መፅሐፉ፣ ጉልበታም
‹‹ገዥ›› አድርጎ በሳላቸው ገፀ-ባሕሪያት አማካኝነት ‹‹…አንዳንድ እንስሳት (ሰዎች) ግን የበለጠ እኩል ናቸው››
ይለናል፡፡ በርግጥ ሁለቱም አይነት አስተዳደሮች መሬት ወርደው ዓለማችንን ዲሞክራት እና አምባ-ገነን
በማለት በሁለት ጎራ የከፈሉ የመሆናቸው ጉዳይ አከራካሪ አይደለም፡፡ ራሷ አሜሪካንን ጨምሮ አብዛኛው
የአውሮፓ አገራት ከሞላ ጎደል በዜጎች እኩልነት ላይ የተመሰረተ ማሕበረሰብ መገንባት ከቻሉት ውስጥ
ሲመደቡ፤ ብዙሃኑ የአፍሪካ እና የእስያ መንግስታት ደግሞ ‹‹አንዳንድ ሰዎች ይበልጥ እኩል ናቸው›› በሚል
መንፈስ የተቃኘ አገዛዝ አንብረው፣ የትኛውንም ተግዳሮት በጠብ-መንጃ ዓይን መመልከትን ፈቅደዋል፡፡ ከእነዚህኞቹ መካከል የእኛይቷ
ኢትዮጵያ ዋነኛዋ ናት፡፡
ባለፉት ሁለት አስርታት በጠቅላይነት የጨዋታ ሕግ እየተመራ፣ ከሰሜን-ደቡብ የተንሰራፋ መዋቅር መዘርጋቱ የተሳካለት ኢህአዴግ፤
የፖለቲካ ሳይንስን በአብዮታዊነት ለውጦ፣ ሀገሪቱን ለጥቂቶች የፌሽታ፣ ለብዙሃኑ የዋይታ መድረክ ሲያደረጋት አንዳች ኮሽታ
ያለመሰማቱ መነሾም ይኸው ነው፡፡ ለሕግ ከማይገዙ ፖለቲከኞች እና ወዳጅ ዘመዶቻቸው አንስቶ፣ በአንድ ጀንበር ሰማይ-ጠቀስ ህንፃን
እንደጓሮ አትክልት የሚያፀድቁ ‹‹አባ-መላዎች›› መበርከታቸው አስማታዊ-ጥበብ ያልሆነብንም ለዚሁ ነው፡፡ የሁለተኛ ደረጃ
ትምህርታቸውን እንኳ ያላጠናቀቁ አፍላ-ወጣቶች ከሁለት ሚሊዮን ብር በላይ ዋጋ ባላቸው መኪኖች መምነሽነሻቸውም ሆነ፣ ለአቅመ
አዳም ሳይደርሱ ግዙፍ የአስመጪና ላኪ ድርጅት ባለቤት ሆነው ማየታችን ይህንኑ ያስረግጥልናል፡፡
አብዮታዊ ግንባሩ ከፊተኞቹ ንጉሳዊም ሆነ ወታደራዊው አስተዳደር የሚለይበት ክፉ ገፅታዎች አሉት፡፡ ለአብነትም ከአጀንዳችን ጋር
በሚዛመደው የፍትሕ ሥርዓት ማነፃፀር ይቻላል፡፡ በአፄው ዘመን በአንፃራዊነት የሰፈነው የሕግ የበላይነት በሂደት ተንኮታኩቶ
ቢወድቅም፤ ደርግ በጎዳና ላይ የፈፀመው ዘግናኙ የቀይ ሽብር ጭፍጨፋ ምዕራፍ ከተዘጋ በኋላ ባሉት የሥልጣን ዘመናቱ፣ በእውቀት
የበቁ እና ከአድሏዊነት የራቁ ሊባሉ የሚችሉ ዳኞች እና ዐቃቢያነ-ሕግ በመሾም፣ ዛሬ ካለው የተሻለ ተቋማዊ የፍትሕ ስርዓት ለመገንባት
መሞከሩን የጊዜው መዛግብት ያወሳሉ፡፡ ከዚህ ባሻገር በሕግ ባለሞያዎች እንደመልካም ነገር የሚጠቀሰው ‹‹ጠቅላይ ዐቃቤ-ሕግ›› ተብሎ
አንድ ሰው ተመርጦ የሚሾምበት አሰራር ነበር፡፡ ምክንያቱም በዚህ ቦታ የሚመደብ ግለሰብ የሀገሪቱን መሪዎችን ጭምር መክሰስ
የሚችልበት ተቋማዊ ሥልጣን ያለው ከመሆኑም በላይ ‹‹አደገኛ ናቸው›› የተባሉ የህትመት ውጤቶችንም ሲያምንበት ሳይሰራጩ ቀድሞ
እስከማገድ የሚያደርስ ሥልጣን ነበረውና፡፡ ይህ አይነቱ አሰራር በምዕራባዊያን ሀገራት የተለመደ ሲሆን፤ የቀጥታ ሥርዓታዊ
ተጠያቂነትንም ስለሚያስከትል በተወሰነ ደረጃም ቢሆን ሕግ ለማስከበር ጠቃሚ መሆኑ በዘርፉ ምሁራንም ዘንድ የታመነበት ነው፡፡
በደርግ ዘመን (ለርዕሰ-ብሔሩ ታማኝ የመሆን ግዴታውን ሳንዘነጋ) ለክስ የሚያበቃ ማስረጃ ካገኘ፣ በየትኛውም የሥልጣን እርከን ላይ
ያለ ሹመኛን በሙሉ ፍርድ ቤት ከመገተር የማያስመልስ ሥልጣን እንደነበረው ይነገራል፡፡
ይሁንና ይህ ሁናቴ የግርንቢጥ ተመንዝሮ የፍትህ ስርዓቱን ከማፀየፍም ተሻግሮ፣ በሕግ ፊት እኩል ያልሆኑ ወይም በኦርዌላዊያን
ቋንቋ ይበልጥ እኩል የሆኑ ‹‹ዜጐች› ተበራክተው የታዩት በዘመነ-ኢህአዴግ ነው ብል ብዙም ስሁት ድምዳሜ አይሆንም፡፡ ከዓመታት
የጥምዝምዞሽ ጉዞ በኋላም የተቀደሰችዋ የፍትሕ ምኩራብ ረክሳ፣ የዜጎች መብት ተደፍጥጦ፣ ‹‹ሕገ-አራዊት›› ገንግኖ፣ ጠብ-መንጃ
መንገሱ ሊስተባበል የማይችል ሀቅ ሆኗአል፡፡
በርግጥ ከሁሉም አስከፊውና አሳሳቢው ጉዳይ የፍትሕ ሥርዓቱ ለዝግመታዊ ሞት መዳረጉ ነው፡፡ ይህንን እውነታ ፕሮፍ መስፍን
ወልደማርያም ‹‹አገቱኒ›› በተሰኘው መጽሐፋቸው የነገሩን ግላዊ ገጠመኝ በሚገባ ከማስረዳቱም ባሻገር፤ ይህን ዘመን ካለፈው ዘመን
እንድናነፃፅረው ዕድል ይሰጠናልና ልጥቀሰው፡-
“ሁለት በጣም የተለያዩ አሰራሮች አጋጥመውኛል፤ መጀመሪያ በአፄ ኃይለሥላሴ ዘመን ተይዤ ነበር፤ በአንድ መጻሕፍት ቤት ቆሜ
ስመለከት አንድ ሰው መጣና መታወቂያውን ከአሳየኝ በኋላ መጥሪያ ወረቀት አሳየኝ፤ እንሂድ ብሎ ይዞኝ ሄደና በወንጀል ምርመራ
አንድ ክፍል ውስጥ አስገባኝ፤ ሁለተኛው በወያኔ ዘመን በ1992ና በ1998 የተያዝኩበት ነው፤ ሁለቱንም ጊዜ ከአስር እስከ አስራ አምስት
የሚሆኑ የታጠቁ ወታደሮች ነበሩ፤ በ1992 የተያዝኩት አንድ የመጻሕፍት መደብር ውስጥ ቆሜ ነበር፤ ከአስር እስከ አስራ አምስት
የሚሆኑ የታጠቁ ወታደሮች በአካባቢው ተበታትነው ለጦርነት የተዘጋጁ ሆነው ሲጠብቁ ሶስት ያህሉ በመጻሕፍት ቤቱ ገብተው
ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ

ከሰማያዊ ፓርቲ የሰላማዊ ሰልፍ አስተባባሪ ኮሚቴ ለመምህራን የተላለፈ ጥሪ

0
0

 

ለተከበራችሁ የኢትዮጵያ መምህራን በሙሉ!!! ለአንድ አገር ብልጽግና ትምህርት ቁልፍ ስለመሆኑ ለማንም አጠያያቂ አይደለም፡፡ ለዚህም ሲባል መንግስታት ለትምህርት የሚሰጡት ትኩረት በቀዳሚነት ቦታ ላይ ይገኛል፡፡ በአገራችን ያለው ነባራዊ ሁኔታ ግን ከዚህ ጋር በእጅጉ የሚቃረን ነው፡፡ የትምህርት ፖሊሲ ከመቸውም ጊዜ በባሰ ሁኔታ ለእናንተ ለመምህራኖች የማያሰራ፣ ብቁ የተማረ ዜጋ የማይፈራበትና ለአገርም የማይጠቅም ሆኗል፡፡ ሁሉንም ነገር ለስልጣናቸው በሚያመች መልኩ የሚዘውሩት የወቅቱ ገዥዎች ትምህርት ከንጉሱና በደርግም ጊዜ ከነበረው በባሰ ደረጃ እንዲገኝ አድርገውታል፡፡ ውድ የአገራችን መምህራኖች፤ በአሁኑ ወቅት መምህር በደርግና በኃይለስላሴ ዘመን ከነበረው ክብር ስለመውረዱ ከእናንተ ውጭ እማኝ መጥራት አያስፈልግም፡፡ መምህራኖች በማስተማር ብቃታቸውና ትምህርት ደረጃቸው፣ በስራ ዘመናቸው፣ በአጠቃላይ ለቀጣዩ ትውልድና ለአገራቸው በሚያበረክቱት ሳይሆን ለስርዓቱ ባላቸው ቅርበትና ርቀት እንደሚመዘኑም እናንተው ራሳችሁ የምታሳልፉት የዕለት ተዕለት ጭቆና በመሆኑ ሀቁ ከእናንተ የተደበቀ አይደለም፡፡ በስራችሁ ላይ የሚደረግባችሁ ጣልቃ ገብነት ተባብሶ መቀጠሉም የአደባባይ ሚስጥር ሆኗል፡፡ የገዥው ፓርቲ ያልተማረ ካድሬ ከእናንተ የተሻለ ተጠቃሚ በሆነበት አገር መጭውን ትውልድ የምትቀርጹት እናንተ መምህራን ግን ኑሮን ለመግፋት ተቸግራችኋል፡፡ በደሞዝ ጭማሬ ስም የ70 ብር ያልበለጠ ጭማሪ ልክ እንደ ቀሪው ጭቁን የኢትዮጵያ ህዝብ በእናንተም ላይ ስርዓቱ እየቀለደ ቀጥሏል፡፡ በነጻነት ለማስተማር አለመቻላችሁና እንዲሁም የሚገባችሁን ክብርና ክፍያ ባለማግኘታችሁ ተሸማቅቃችሁ እንደምትኖሩ የታወቀ ሀቅ ነው፡፡ መምህር ለራሱ ብቻ ሳይሆን አገሩንና ቀጣዩን ትውልድም የሚቀርጽ ፈጣሪ የማህበረሰባችን ክፍል ነው፡፡ ሆኖም የኢትዮጵያ መምህራን ስለ ራሳችሁ መብት እንኳ ጮኽ ብላችሁ ስትከራከሩ፣ ስታስተምሩ አይታይም፡፡ ከስርዓቱ አፋኝነት አንጻር ለእናንተ የሚከራከሩ ማህበራትም የሉም፡፡ በጣም የሚያሳዝነው በ1960ዎቹ እነዚህ ማህበራት ለአባላቶቻቸው ከመቆም አልፈው ለአገራቸው ህዝብ ድምጽ እንደነበሩ ስናስብ ነው፡፡ በዛ ዘመን ከየትኛውም ተቀጣሪ በላይ ሲከበርና ሲከፈለው የነበረው መምህር ‹‹እኔ ተጠቃሚ ነኝ!›› ብሎ የህዝቡን ችግር ጀሮ ዳባ ልበስ ብሎ አላለፈም፡፡ በአሁኑ ወቅት እናንተም ችግር ውስጥ ወድቃችሁ፣ አገራችንም በሚያሳዝን ምስቅልቅል ላይ ሆና ድምጻችሁ አይሰማም፡፡ መብታችሁ ሲነጠቅ፣ ህዝብ መብቱን ሲቀማ፣ ከቀዬው ሲፈናቀል፣ አገራችን ስትዋረድ….በርካታ በደልና ግፍ ሲደርስ ማስተማር፣ መተቸት፣ ጮህ ብሎ መናገር የነበረበት መምህር የጋን መብራት ሆኗል ማለት ይቀላል፡፡ ፓርቲያችን ሰማያዊ መምህራንን ጨምሮ የአገሪቱ ህዝብ በአሳዛኝ ጭቆና ላይ በመሆኑ የተነጠቁትን መብቶች ለማስመለስ ሚያዝያ 19/2006 ዓ.ም ታላቅ ሰላማዊ ሰልፍ ጠርቷል፡፡ በዚህ ሰልፍ የተነጠቃችሁትን የማስተማር ነጻነት፣ ክብር፣ እንዲሁም እንደ አንድ ኢትዮጵያዊ ዜጋ ያጣችኋቸውን መብቶች ጮህ ብላችሁ እንድትናገሩ፣ ህዝብ መብቱን በነጻነት መጠየቅ እንደሚችል እንድታስተምሩ ጥሪ አቅርቦላችኋል፡፡ መምህር የጋን መብራት በሆነባት አገር ትውልድ ወደባሰ ጨለማና ጭቆና ማምራቱ የማይቀር በመሆኑ መምህራን የሙያም ሆነ አገራዊ ግዴታችሁን በመወጣት የእናንተንም ሆነ የቀሪውን ኢትዮጵያዊ ወገናችሁን መብት ለማስመለስ በምናደርገው የትግል ጉዞ ግንባር ቀደሙን ስፍራ ይዛችሁ ህዝብ እንድታታግሉ በድጋሚ ጥሪ እናቀርባለን፡፡

ሰበር ወቅታዊ ፖለቲካዊ ሁኔታዎች –ኢህአዲግ እና ተቃዋሚዎች ወሳኝ ነጥብ ላይ ናቸው

0
0

ከጌታቸው በቀለ
eggtሰበር ወቅታዊ ፖለቲካዊ ሁኔታዎች – ኢህአዲግ እና ተቃዋሚዎች ወሳኝ ነጥብ ላይ መሆናቸውን አውቀውት ይሆን? የግብፁ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር እና የደህንነት ኃላፊ ዋሽግተን ገቡ፣የመካከለኛው ምሥራቅ ትኩሳት ተቀስቀሰ፣ሩስያ ከመቸውም በበለጠ ደረጃ እየተፈራች ነው።(የጉዳያችን አጭር ማስታወሻ)

 

የዓለማችን ዓለም አቀፋውም ሆነ አካባቢያዊ ሁኔታዎች በፍጥነት እየተቀየሩ ነው።የዩክሬኑ ጉዳይ ከመሻሻል ይልቅ ከቀን ቀን እየተባባሰ መጥቷል።ሩስያ ከክሬምያ ህዝበ ውሳኔ በኃላ የምዕራባውያን ቁጣ ወደ ጎን በማለት ዩክሬን ያሉ አፍቃሪ-ሩስያውያንን ሁኔታ በአንክሮ እየተከታተለች ነው።ዛሬ ዩክሬን  በአፍቃሪ-ሩስያውያን ላይ በወሰደችው እርምጃ ከአምስት ያላነሱ መገደለቸው ሩስያን በእጅጉ ከማስቆጣቱም በላይ በዩክሬን ድንበር ላይ የጦር ልምምድ እያደረገች መሆኗ ተገልጧል።የሩስያው ውጭ ጉዳይ ሚኒስትርም በድጋሚ (ዛሬ) ለዩክሬን ማስጠንቀቅያ ሰጥተዋል።ሌላው አስገራሚ ጉዳይ ደግሞ ትናንት ቢቢሲ በድረ-ገፁ እንደገለፀው ‘የእንግሊዝ አየር ኃይል የሩስያ አየር ኃይል የእንግሊዝን የአየር ክልል ለመጣስ ሲሞክር ተደረሰበት የሚል ዜና መልቀቁ ሲሆን ጉዳዩ ወደ መጎናተል ተሽጋገረ እንዴ? ለማለት ያስገድዳል።

የግብፁ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር እና የደህንነት ኃላፊ ዋሽግተን ገቡ

ይህ በእንዲህ እንዳለ ከግብፅ አብዮት ወዲህ ለመጀመርያ ጊዜ ከፍተኛ የተባለ የግብፅ ባለስልጣናት ወደ ዋሽግተን ለምክክር ተጉዘዋል።ባለስልጣናቱ የግብፅ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ናቢል ፋህሚ እና የደህንነት መስርያቤቱ ኃላፊ ሜጀር ጄነራል ሞሐመድ ኤል ቶሃሚ ሲሆኑ ከአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጆን ኬሪ ጋር ዝግ ውይይት እንዳላቸው ”አህራም ኦን ላይን” በድረ-ገፁ ገልጧል።አሜሪካ ባለፈው ሐምሌ ወር ለግብፅ ትሰጥ የነበረውን የወታደራዊ እርዳታ እንደገና እንደምትገመግም መግለጧ ይታወቃል።የሁለቱ ባለስልጣናት ጉብኝት ዋና አላማ አሜሪካን ለግብፅ ለመስጠት ተዘጋጅታ የነበሩና ያዘገየቻቸውን ታንኮች፣ሚሳኤሎች፣ተዋጊ አይሮፕላኖች እና ሄሊኮፕተሮች እና በተጨማሪም 260 ሚልዮን ዶላር የጥሬ ገንዘብ ዕርዳታ እንድትለቅ ለማግባባት ጭምር እንደሚሆን ድረ-ገፁ ገልጧል።ከእዚህ በተለየ ድረ-ገፁ አይግለፀው እንጂ የግብፅ የወቅቱ ቁጥር አንድ አጀንዳ በኢትዮጵያ እየተሰራ ያለው የአባይ ግድብ ጉዳይ እንደሚነሳ መገመት ይቻላል።

የመካከለኛው ምሥራቅ ትኩሳት ተቀስቀሰ

በሌላ በኩል ለዘመናት የአፍካ ቀንድ ሃገራትን እና ግብፅ ከአሜሪካን እና እስራኤል ጋር የሚኖራቸውን የግንኙነት መስመር የሚያዋልለው የመካከለኛው ምስራቅ ትኩሳት የመጨመር አዝማምያ እንደሚኖር የሚያመላክት አዲስ ክስተት መታየት ጀምሯል።ይሄውም የፍልስጤም ሁለቱ ባላንጣ ቡድኖች ማለትም በምዕራቡ በሚደገፈው የፍልስጤም ራስ ገዝ መንግስት እና በነውጥ የሚያምነው ‘በሐማስ’ መካከል ለእረጅም ጊዜ ሲደረግ የነበረው ውይይት ሰምሮ የመስማማታቸው ዜና ነው። አሜሪካ እና እስራኤል ከሐማስ ጋር የሚደረግ ማናቸውም ስምምነት እንደማይደግፉ በግልፅ አሳውቀዋል።እስራኤል በተለይ ከፍልስጤም ራስ ገዝ መንግስት ጋር የነበረውን ውይይት ለማቆም መገደዷን ገልፃለች። ይህ ማለት የመካከለኛው ምስራቅ የኃይል አሰላለፍ እንደገና አጃቢ ስልታዊ ሃገራትን ይዞ መቀስቀሱን ያመላክታል።የኃያላን ሃገራትም ትኩረት በአዲስ መልክ ከመሳቡ ባለፈ ትናንሽ የሚባሉ ሀገራትንም ስቦ ማስገባቱ አይቀርም።

ኢህአዲግ እና ተቃዋሚዎች ወሳኝ ነጥብ ላይ መሆናቸውን አውቀውት ይሆን?

ከላይ የተገለፁት የሩስያ የልዕለ ኃይልነት ስሜት መነቃቃት እና የመካከለኛው ምስራቅ ፖለቲካ መጋጋል የግብፅን ስልታዊነት አስፈላጊነት መጨመሩ እና ኢትዮጵያ ደግሞ ከግብፅ በበለጠ በአባይ ጉዳይም ሆነ በአፍሪካ ቀንድ ባላት የህዝብ ብዛት እና ወሳኝ ስልታዊ አቀማመጥ አስፈላጊነቷ መጨመሩ የማይቀር ብቻ ሳይሆን የምዕራባውያንን ትኩረት መሳቧ ሃቅ ነው። ይህ ማለት በኢትዮጵያ የሚነሳ ማናቸውም ተፅኖ ፈጣሪ የመደመጥ ኃይሉ ቀላል አይሆንም ማለት ነው። የአካባቢው ትኩሳት በመካከለኛው እና በሩስያ ጉዳይ ብቻ አይሳብም የደቡብ ሱዳን እና የሱማልያው ጉዳይ ገና  አቅጣጫቸው በአግባቡ ያልለየላቸው መሆኑ እና ኢትዮጵያ አሁንም ወሳኝ መሆኗን ማሰብ ይገባል።እዚህ ላይ የኤርትራ ዕድልም እራሱ የሚታየው የአዲስ አበባ ፊት እየታየ መሆኑ እውነታው ነው።እነኝህ ሁሉ ሁኔታዎች የኢትዮጵያ የፖለቲካ መድረክ መረጋጋት እና ወሳኝ ደረጃ ላይ መድረስ እንዳለበት ለማመን ሊቅ መሆን አይጠይቅም።

በኢትዮጵያ ኢህአዲግ የህዝቡን ስሜት እና የፖለቲካ ሳይንስ ተከትሎ ለለውጥ አለመዘጋጀቱ እና የጎሳ ፖለቲካውን ከሚገባው በላይ መወጠሩ ኢትዮጵያ አስፈሪ ሁኔታ እንዳይፈጠር ያሰጋል።ይህንን ስጋት ማስወገድ ማለት ደግሞ በመካከለኛው ምስራቅ ላይ ሚና የምትጫወተውን ግብፅን ብቻ ሳይሆን የቀይ ባህርንም የመቆጣጠር ዕድል መሆኑን ወዳጅም ጠላትም የሚረዳው ጉዳይ ነው።ጠላት ከመቼውም በበለጠ ሁኔታ ኢትዮጵያን በጎሳ ለማተራመስ ሲሰራ ወዳጅ ደግሞ የኢትዮጵያን ታሪካዊ የፖለቲካም ሆነ ወታደራዊ የበላይነቷን እንድትይዝ ይሰራል።ከእዚህ በተለየ ደግሞ  ባእዳን ጥቅማቸውን በማንኛውም መንገድ ከሚያስከብርላቸው ጋር ለመስራት ይተጋሉ።ጥያቄው ለኢትዮጵያ የተሻለ ዕድል የሚፈጥረውን መንገድ መርጦ የሚሄድ መንግስት አላት ወይ? የሚል እና ተቃዋሚው ኃይልስ ምን እየሰራ ነው? የሚሉ ወሳኝ ጥያቄዎች ናቸው።

ለኢትዮጵያ ያሏት እድሎች ሁለት ናቸው።አንድኛው-ኢህአዲግ እራሱ ለለውጥ ማዘጋጀት እና ኢትዮጵያ ያላትን መልካም ዓለም አቀፋዊና አካባቢያዊ ዕድል እንድትጠቀም ”360 ዲግሪ የዞረ” የፖሊሲ ለውጥ ማሳየት እና ቅድምያ ለሃገር ቢሰጥ ያለንበትን ታሪካዊ ዕድል ለመጠቀም መቻል ነው።ካለፉት የኢህአዲግ ተግባራት ተነስተን ይህ ለብዙዎቻችን ሕልም ነው።ኢህአዲግ ለሀገር ቅድምያ ባለመስጠት ዝናን ያተረፈ ነው።ይህ ካልሆነ ግን ጉዳዩ ያለው ተቃዋሚ ኃይሎች ጋር ነው ማለት ነው። የኢትዮጵያ የተቃውሞ ኃይላት እራሳቸውን በፍጥነት የሚያስተባብሩበት ጊዜ ነገ ሳይሆን ዛሬ መሆኑን መረዳት ይቻላል።ተቃዋሚ ኃይሎች ልዩ የሆነ ህብረት እና አዲስ አቀራረብ ይዘው ከሰሞኑ መገኘት እና ለልዕለ ሃያላኑንም ሆነ የኢትዮጵያ ጉዳይ ለሚያሳስበን ዜጎች ሁሉ ከጊዜያዊ ሕብረት ይልቅ ፍፁም የሆነ አንድነት እና የለውጥ ስልት ሊያሳዩን ይገባቸዋል።ዓለም አቀፋውም ሆነ አካባቢያዊ ፖለቲካዊ ሁኔታ የሚያመላክተው ይህንኑ ነው።ጊዜ ያለ አይመስልም።

ጉዳያችን
ሚያዝያ 16/2006 ዓም

ይህ ጽሁፍ በጉዳያችን ብሎግ ላይ ታትሟል።
 

Posted by Tadesse Yimer

 

የፋሲካ ዕርቅን ከሰሜን አየርላንድ ብንማርስ?   (በ-ዳጉ ኢትዮጵያ) 

0
0

(በ-ዳጉ ኢትዮጵያ
(dagu4ethiopia@gmail.com)

 

የፋሲካ ዕርቅን ከሰሜን አየርላንድ ብንማርስ?                              
ከ16 አመታት በፊት እንደ አውሮፓውያን አቆጣጠር ሚያዚያ 10 ቀን 1998፡፡ በሰሜን አየርላንድ የሰላም ሒደት ውስጥ ቁልፍ ቦታ የሚሰጠው የዕለተ ስቅለት ስምምነት (The Good Friday Agreement) ተፈረመ፡፡ ከረጅም ጊዜ የእርስ በዕርስ ጦርነት፣ ካልተቋረጠ ውጥረትና የእርስ በእርስ ጥላቻ በኋላ የተፈረመው ይህ ውል በውስጡ ሁለት ተዛማጅ ስምምነቶችን የያዘ ነበር፡፡ ቀዳሚው በአብዛኛዎቹ የሰሜን አየርላንድ ፓርቲዎች መካከል የተደረገ ስምምነት ሲሆን ሌላኛው ደግሞ በእንግሊዝና በአየርላንድ መንግስታት መካከል የተደረገው አለም ዓቀፍ ስምምነት ነበር፡፡

በተለምዶ The Troubles እየተባለ የሚጠራው የሰሜን አየርላንድ ግጭት ከ1960ዎቹ ጀምሮ በሰሜን አየርላንድ ውስጥ ሲካሔድ የቆየ የብሔር ግጭት ሲሆን አድማሱንም በማስፋት አየርላንድ ሪፑብሊክን፣ ኢንግላንድን ብሎም መላውን አውሮፓ ያዳረሰ የዘመናዊቷ አውሮፓ የከፋ ግጭት ነበር፡፡ ግጭቱ በዋነኝነት ፖለቲካዊ መልክ ሲኖረው ብሔረሰባዊ ገጽታም ነበረው፡፡

የግጭቱ ዋነኛ ማጠንጠኛ የሰሜን አየርላንድ ህገመንግስታዊ ቦታ (constitutional status) እና በሁለቱ ዋና ዋና የሰሜን አየርላንድ ማኅበረሰቦች፣ ማለትም ከዩናይትድ ኪንግደም ጋር በአንድነት መኖር በሚፈልጉት በአብዛኛው የፕሮቴስታንት እምነት ተከታዮችና የተዋሐደችውን አየርላንድ መመስረት በሚፈልጉት በአብዛኛው የካቶሊክ እምነት ተከታይ በሆኑት የአይሪሽ ብሔረተኞች መካከል የሚኖረው ግንኙነት ነበር፡፡

ልክ የዛሬ 16 ዓመት በእለተ ስቅለት ከ3,500 በላይ ለሆኑ ሰዎች መሞትና ከ50 ሺ በላይ ለሆኑት መቁሰል ምክንያት የሆነው ግጭት በስምምነት እልባት ተበጀለት፡፡ ክርስቶስ አለሙን ከእግዚአብሔር ጋር ያስታርቅ ዘንድ ቤዛነትን በከፈለበት ቀን በወንድማማቾች መካከል ያለን ፀብ በዕርቅ መፍታት ምንኛ የተወደደ ተግባር ነው!

በቅዱስ መጽሐፍ በኤፌሶን ምዕራፍ 2 ቁ. 14 ላይ “እርሱ ሰላማችን ነውና፤ … በመካከል ያለውን የጥል ግድግዳን በሥጋው ያፈረሰ…” ሲል የክርስቶስን ቤዛነት ምስጢር ይነግረናል፡፡ እያከበርነው የምንገኘው የክርስቶስ ስቅለትና ትንሳዔ በአል በዋነኝነት በእግዚአብሔርና በሰው መካከል ስላለው የጥል ግርግዳ መፍረስ ቢሆንም የሰሜን አየርላንድን አርአያ ተከትለን በመካከላችን ያለውን ፀብና አለመስማማት ለመፍቻ ብንጠቀምበት የበለጠ ግሩም ይሆናል፡፡

በወንድማማቾች መካከል ያለው የፀብ ግርግዳ ይፈርስ ዘንድ ዶ/ር ደብረ ጽዮን ከዶክተር ብርሐኑ፣ አቦይ ስብሀት ከፕሮፌሰር መስፍን፣ ጄ/ል ሳሞራ ለጄ/ል ከማል መተቃቀፍ ባይችሉ እንኳን በክብ ጠረጴዛ ዙሪያ ስለችግሮቻቸው መፍትሔ ሲወያዩ ብናይ የክርስቶስ ትንሳዔ በዓልን ከሐገራችን ትንሳኤ ጋር አያይዘን ባከበርነው ነበር!

በአንድ ሐገር ልጆች መካከል ያለው የጥል ግርግዳ ይፈርስ ዘንድ ገዢው ፓርቲ በማጎሪዎቹ ያያዛቸውን መብታቸውን ከመጠየቅ ባለፈ አንዳች ወንጀል ያልሰሩ የህሊና እስረኛ ወንድሞቻችንና እህቶቻችንን በዓሉን በማስመልከት ቢፈታልን የበአሉን መልዕክት ምንኛ በላቀ መልኩ መረዳት በሆነ ነበር! አንዱአለም አራጌ፣ ርዕዮት ዓለሙ፣ ኦልባና ሌሊሳ፣ እስክንድር ነጋ፣ የሙስሊም መፍትሔ አፈላላጊ ኮሚቴ አባላት… ወዘተ እና ሌሎች የማናውቃቸው በየሰቆቃ ጣቢያው ፍትህ ተነፍገው የሚሰቃዩ ሺህ በሺ ወገኖቻችን ከዕርቅና ስምምነት በመነጨ የነጻነትን አየርን ሲተነፍሱ ብናይ የክርስቶስን የዕርቅ መልዕክት በላቀ ጥልቀት በመረዳት በታሪክ ድርሳናት ላይ መስፈር በቻልን ነበር!

የእምነት አባቶቻችን ቀኑን አስመልክተው ለምዕመናኖቻቸው በሚያስተላልፏቸው መልዕክቶቻቸው ለዚህ ዓመት እንኳን መንግስትን ለማስደሰት ከሚደረጉ የካድሬ መሠል መልዕክቶች ተላቀው በገዢውም ሆነ በተቃዋሚው ወገን ላሉ ሁሉ ይህን የእርቅ መልዕክት ቢስተላልፉ ምንኛ በኮራንባቸው ነበር!

በተቃዋሚው ጎራ ያሉትም መሪዎች አንድ መሆን ባይችሉ እንኳን በመከባበርና በመተባበር በጋራ ይሰሩ ዘንድ በስምምነት ሲጨባበጡ በጋዜጦች የፊት ሽፋን ላይ ብንመለከት፣ የሰማያዊው ኢ/ር ይልቃል ከአንድነቱ ኢ/ር ግዛቸው፣ የኦፌኮው ዶ/ር መረራ ከመኢአዱ አቶ አበባው ጋር በወንድማማችነት መንፈስ አብረው ለመስራት ሲስማሙ ብናይ የወንድማማቾች የፀብ ግድግዳ ስለመፍረሱ ምንና ህያው ምስክርነታችንን በሰጠን ነበር!

መልካም ፋሲካ!

 

የጃኪ ጎሲ የሕግ አማካሪ ተናገሩ፡ “ሸዋ ከዚህ ቀደም ቴዲ አፍሮን፣ ሔኖክ አበበንና ጆኒ ራጋን ከሷል”፤ በሸዋ ላይ የ$400,000 ካሳ ክስ አቅርበናል

0
0

የጃኪ ጎሲ የሕግ አማካሪ ተናገሩ፡ “ሸዋ ከዚህ ቀደም ቴዲ አፍሮን፣ ሔኖክ አበበንና ጆኒ ራጋን ከሷል”፤ በሸዋ ላይ የ$450,000  ካሳ ክስ አቅርበናል
(ዘ-ሐበሻ) ከደቂቃዎች በኋላ የጃኪ ጎሲ የዋሽንግተን ዲሲ ኮንሰርት ከመጀምሩ አስቀድሞ ከዘ-ሐበሻ ጋር ቃል የተመላለሱት የጃኪ ጎሲ የህግ አማካሪ የሆኑት አቶ መንግስቱ አስፋው የፍርድ ሂደቱ የጃኪ የሰሜን አሜሪካ ኮንሰርቶች ከመደረጋቸው በፊት ቢጠናቀቅ እንኳ የሌሎች ከተማዎችን ኮንሰርቶች ምንም የሚያሰጋ ነገር እንደለሌለና በተሳካ ሁኔታ እንደሚደረጉ አስታወቁ። የሕግ አማካሪው “ለጃኪ ክስ መከላከያዎችን ስናሰባስብ ከዚህ ቀደም ሸዋ ኢንተርቴይመንት በቴዲ አፍሮ፣ በሄኖክ አበበና በጆኒ ራጋ ላይ ክስ መመስረቱን ማስረጃውን አግኝተናል” ካሉ በኋላ በተለይም ሄኖክ አበበና ጆኒ ራጋ በዋሽንግተን ዲሲ በሸዋ የተነሳ የደረሰባቸውን ሸዋ የጃኪን ኮንሰርትም ለማሰናከል 11ኛው ሰዓት ላይ ክስ መመስረቱን በማስታከክ አብራርተዋል።

ሸዋ ኢንተርቴይመንት በፍርድ ቤት የጃኪን ስም በመጥፎ ነገር እንዳያነሳ ተነግሮት እያለ በዘ-ሐበሻ ላይ ወጥቶ የተናገረው በሕግ ሊያስጠይቅ እንደሚችል የጠቆሙት አቶ መንግስቱ የጃኪ ኮንሰርትን ለማሰናከል ባደረገው ጥፋት እስከ 400 ሺህ ዶላር በሚጠጋ የካሳ ክፍያ በሕግ ጠይቀነው ጉዳዩ በፍርድ ቤት ተይዟል ብለዋል። ሸዋ ኢንተርቴይመንትም በተመሳሳይ የ$500 ሺህ ዶላር የካሳ ክፍያ ክስ መመስረቱን ለዘ-ሐበሻ መግለጹ ይታወሳል። አቶ መንግስቱ በጃኪ ጎሲና ኢቫንጋዲ ፕሮዳክሽንን ወክለው ለዘ-ሐበሻ የሰጡትን ቃለምልልስ ይከታተሉት።

ሰማያዊ ፓርቲ ዛሬ በአዲስ አበባ የጠራው ሰልፍ ተጠናቀቀ፤ ሕዝቡ አደባባይ ወጥቶ “ውሃ ጠማን”አለ

0
0

(ዘ-ሐበሻ) ሰማያዊ ፓርቲ ዛሬ በአዲስ አበባ ከተማ የጠራውን ‘የተነጠቁ መብቶቻችንን እናስመልስ” ሰላማዊ ሰልፍ በብዙ አፈና ታጅቦ ማጠናቀቁን ለዘ-ሐበሻ የደረሰው መረጃ አመለከተ። በተደጋጋሚ በዚህ ሳምን በድረገጻችን ላይ እንደዘገብነው የዛሬውን ሰላማዊ ሰልፍ ለማሳካት የሰማያዊ ፓርቲ አባላት በአዲስ አበባ ከተማ ቅስቀሳ በሚያደርጉበት ወቅት እስር እና እንግልት ሲደርስባቸው ቆይቷል።

ዛሬም መነሻውን ከፓርቲው ጽ/ቤት ተነስቶ በአዋሬ፣ አድዋ ድልድይ፣ ባልደራስ አድርጎ መድረሻው ወረዳ 8 ሜዳ የካ ሚካኤል ታቦት ማደርያ ባደረገው ሰላማዊ ሰልፍ ላይ ፖሊስ በሰላማዊ ሰልፈኞች ላይ የማንገላታትና የማሸማቀቅ ሥራዎችን ሲሰራ እንደነበር የዘ-ሐበሻ ዘጋቢዎች ጠቁመዋል።

በአዲስ አበባ ያለውን የመብራት እጦት፣ የትራንስፖርት፣ የውሃ እጦት፣ የኔትወርክ እጥረትና ሌሎች የማህበራዊ ቀውሶችን ያስተጋባው የዛሬው የሰማያዊ ፓርቲ ሰላማዊ ሰልፍ ላይ ከተሰሙት መፈክሮች መካከል
“ውሃ ጠማን ውሃ ጠማን”
“ፍትህ ናፈቀን ፍትህ ናፈቀን”
“ውሽት ሰለቸን ውሽት ሰለቸን”
“የሙስሊሙ መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ ባስቸኳይ ይፈቱ”
“በቀለ ገርባ አሽባሪ አይደለም”
“ኦልባና ለሌሳ አሽባሪ አይደለም”
“አቡበክር አሸባሪ አይደለም”
“አንዷለም አራጌ አሽባሪ አይደለም”
“እስክንድር ነጋ አሽባሪ አይደለም”
“ናትናኤል መኮንን አሽባሪ አይደለም”
“ርዮት አለሙ ጋዜጠና እንጂ አሽባሪ አይደለችም” የሚሉና ሌሎችም ድምጾች ከሰልፉ ተሳታፊዎች ተደምጠዋል።

በተለይም ተሰላፊው “እኛ ኢትዮጵያኖች አንለያይም፤ እኛ ኢትዮጵያኖች አንድ ነን” የሚሉና “የተነጠቁ መብቶቻችን ይመለሱልን” ሲሉ ጩኸታቸውን ያሰሙ ሲሆን መንግስት የለም ወይ? እያሉም ሲጮኹ ነበር።

በሰላማዊ ሰልፉ ላይ ንግግር ያደረጉትና በቅስቀሳው ወቅት ታስረው ባለፈው አርብ ማምሻውን የተለቀቁት ኢንጂነር ይልቃል ጌትነት ለሰልፈኛው “ወደ ሰልፉ የመጡትን እና ስልፉን ያስተባበሩትን ወጣቶች እና መላውን ባለ መብት ተሳታፊ አመሰግናለሁ። ስርዓቱ በሙስና ተጨማልቋል፡፡ አገራችን አደጋ ላይ ወድቃለች፡፡ ከሰማያዊ ፓርቲ ጋር ሆነን እጣ ፈንታችን እንወስን። በየትኛውም አገር አምባገነን እንዲሁ ለሕዝቡ መብት አይሰጥም። አስፈላጊውን መስዕዋትነት መክፈል አለብን” ብለዋል።

ሊቀመንበሩ ቀጥለውም “ከ19 አመት ጀምሮ እስከ 63 አመት ያሉት አባላትና አመራሮቻችን ታስረዋል፡፡ ክርስቲያኖች፣ ሙስሎሞች ወጣቶች፣ ኢንጅነሮች፣ ሌሎቹም ታስረውብናል። ይህም የኢህአዴግ አምባገነንነት ያሳያል፡፡ ሰማያዊ ለሁሉም የህዝብ ክፍል እንደሚቆምም በዚህ ሰልፍ የታሰሩት አባላትና አመራሮቻችን ማሳያ ናቸው ነው። ክብርና ፍርሃት፣ ማጎብደድ የኢትዮጵያውያን ባህል አይደለም፡፡ ማሸነፍን ያስተማርን ህዝቦች ነን፡፡ ሙስሊም ክርስቲያኑ በጨዋነት አብሮ የሚኖርባት አገር ናት፡፡ እነሱ ግን ይከፋፍሉናል፡፡ አሁን በአዋራጅ ሁኔታ ላይ እንገኛለን። ይህን ለማስቆም ከእነአስፈላጊው መስዋትነት ሌት ተቀን እንሰራለን” በማለት ንግግራቸውን አስመተዋል።

የሰልፉን ሁኔታ የሚያሳውን ፎቶዎች ይመልከቱ
addis ababa semayawi
blu paty8

addis ababa semayawi

blue paty 7

blue party 6

blue party 5

blue party 4

blue party 2

blue 6


“እኛም ከሚሊዮኖቹ ውስጥ ነን” (የኢትዮጵያ ሕዝብ የጋራ ትግል ሸንጎ (ሸንጎ)

0
0

PDF-  ለማንበብ እዚህ ይጫኑ

ሚ ሚያዝያ 19፣ 2006 (ኤፕሪል 27፣ 2014)

የኢትዮጵያ ሕዝብ የጋራ ትግል ሸንጎ (ሸንጎ)፣ በአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት)  እየተቀነባበረ በሚካሄደው “የሚሊዮኞች ድምፅ” ንቅናቄ ውስጥ “እኛምከሚሊዮኞቹ ውስጥ ነን” በማለት ለተጀመረው እንቅስቃሴ ሙሉ ድጋፉን እንደሚሰጥ ሲገልጽ በታላቅ ደስታ ነው። በዚህም መሠረት የዚህ እንቅስቃሴ አካልነታችንንበተግባር ለመግለፅ በአዳማ (ናዝሬት) የሚካሄደውን እንቅስቃሴ በስፖንሰርነት ለመደገፍ ዕድሉ ስለገጠመን እጅግ ደስተኛ ነን።

ሸንጎ በተደጋጋሚ እንደገለጸው፣ በሀገራችን ውስጥ የሰፈነው የግፍ፣ የአድልዖና የከፋፋይነት ሥርዓት ማብቃት አለበት።  ሥርዓቱ የሀገሪቱን ሕዝብና ሁሉንም የሀገሪቱን አካባቢ በከፍተኛ አደጋ ላይ ጥሏል። ኢትዮጵያን የባሕር በር የሌላት ከማድረግ ጀምሮ ዜጎቿን እርስ በርስ በጥርጣሬ እንዲተያዩ  አልፎም እያንዳንዱ ዜጋ ያለፍትኅ እየተጎተተ የሚታሠርበት፣ የሚደበደብበት፣ ከሥራና ከንብረቱ የሚፈናቀልበት ሀገር እስከመሆን ደርሰናል። ገዥው ቡድንና ሥርዓቱ የሚመራበት ፖሊሲና ተግባሩ እንኳንስ ለአብዛኛው ኢትዮጵያዊ ቀርቶ፣ ለራሱ ለሥርዓቱ ደጋፊዎች የማይበጅ እንደሆነ ሁሉም የሚገነዘበው ነው።

ይህ አስከፊ ሁኔታ እንዲያከትምና በሕጋዊና ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት እንዲተካ ለማድረግ ደግሞ በአንድ በኩል የተቃዋሚ ድርጅቶች ተሰባስበው የተቀነባበረ ተግባራዊ እንቅስቃሴ ማካሄድ ሲገባቸው በሌላ በኩል ደግሞ ኢትዮጵያውያን ሁሉ የተጀመሩትን አበረታች እንቅስቃሴዎችን በተግባር እንዲያጠናክሩ ይጠበቃል። በዚህ መልክ ስንሰባስብና ሃላፊነት በመውሰድ ትግሉን ስናጠናክር የወገኖቻችን ስቃይና በሀገራችን ላይ የተጋረጠው አደጋ ማብቂያና የብሩኅ ተስፋ ዘመን መጀመሪያ ጊዜ እጅግ የቀረበ ይሆናል።

ለዚህ ነው ሸንጎው በኢትዮጵያ ሀገራችን አንድነት የሚያምኑትን የተቃዋሚ ኃይሎች በጋራ እንድንሰባሰብ ደግሞ ደጋግሞ የሚጠራው። ለዚህም ነው ሸንጎ “እኛምከሚሊዮኞቹ ውስጥ ነን” በማለት በአንድነት አቀነባባሪነት የተጀመረውን እንቅስቃሴ ሙሉ በሙሉ የሚደግፈው። ለዚህ ነው ሸንጎው ሁሉም ኢትዮጵያዊ የዚህ የነፃነት ትግል አካልነቱንና አጋርነቱን በተግባር እንዲያሳይ  በቀጣይነት የሚጥረውና የሚያበረታታው።

አንድነት ኃይል ነው!

ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!
shengo

ብቸኛው ሰው (ፕሮፌሰር መስፍን ወልደማሪያም)

0
0

ፀሓፊ፡ አፈንዲ ሙተቂ
——–
Afendiፕሮፌሰር መስፍንን በአካል ያየሁት ሁለት ጊዜ ያህል ብቻ ነው፡፡ በነዚህም ጊዜያት ከመጨባበጥ በቀር ሌላ ነገር ማውጋት አልቻልንም፡፡ ብንጨዋወት እንኳ በፖለቲካ አመለካከታችን የምንግባባ አይመስለኝም፡፡ ለምሳሌ እሳቸው “ኢትዮጵያ ውስጥ ነገዶችና ጎሳዎች እንጂ ብሄሮችና ብሄረሰቦች የሉም፤ በኢትዮጵያ ውስጥ ያለው አንድ ብሄር ብቻ ነው” ነው የሚሉት፡፡ እኔ ግን “በኢትዮጵያ ውስጥ ብዙ ብሄሮችና ብሄረሰቦች አሉ፤ ነገድና ጎሳ የብሄር ቅርንጫፎች እንጂ ራሳቸውን የቻሉ ህዝቦች አይደሉም” ነው የምለው፡፡ በሌላ በኩል ፕሮፌሰር መስፍን “የብሄረሰቦችን መብት ለማስከበር በብሄር መደራጀቱ ለሀገር አንድነት አደጋ አለው” የሚል እምነት አላቸው፡፡ እኔ ግን “ለመጥፎ ዓላማ እስካልሆነ ድረስ በብሄር መደራጀቱ መጥፎ አይደለም” የሚል እምነት አለኝ፡፡ ሌላም ብዙ ልዩነት ማስቆጠር ይቻላል፡፡

ይሁንና በፖለቲካ እንዲህ የተለየኋቸውን ምሁር ለአንድም ቀን እንደ ጠላት አይቼአቸው አላውቅም፡፡ በተቃራኒው ህሊናን በሚያምራምሩ ብዙ ባህሪያቶቻቸው በጣም ያስቀኑኛል፡፡ “እኛስ መቼ ነው እንደርሳቸው ሆነን ለሀገራችንና ለህዝባችን ክብር የምንቆረቆረው” እላለሁ፡፡ ከዚህ ፈቅ የሚሉት አንዳንድ አድራጎታቸው ግን በነቢያትና በቅዱሳን ካልሆነ በቀር ከኛ ዘመን ሰው የሚጠበቁ አይደሉም፡፡

በእርግጥ እላችኋለሁ! ፕሮፌሰር መስፍን በብዙ አጋጣሚዎች “ሰው ማለት… ሰው የሚሆን ነው ሰው የጠፋ ዕለት” የተሰኘውን ብሂል በተግባር ከውነው ያሳዩን ብሄራዊ ጀግና ናቸው፡፡ እኝህ ታላቅ ሰው ሀገራችን ሰው በምትፈልግበት ልዩ ልዩ አጋጣሚዎች በልዩ ድፍረትና ልበ ሙሉነት በከወኗቸው ድርጊቶቻቸው የህዝብ ልጅ መሆናቸውን አስመስክረዋል፡፡

ፕሮፌሰር መስፍን ለብቻቸው ሆነው የፈጸሟቸውን በርካታ ገድሎች መዘርዘር እንችላለን፡፡ ለዛሬው ግን በጣም ጥቂቶቹን ብቻ እንዲህ እንዘክርላቸዋለን፡፡

=== የትግራይና ድርቅና ረሃብ===

ብዙዎቻችን በ1965 ስለተከሰተው የወሎ ረሃብ በቂ መረጃ አለን፡፡ ከዚያ አስቀድሞ በ1950ዎቹ ስለተከሰተው የትግራይ ረሃብ ግን ብዙም ሲጻፍ አላነበብኩም፡፡ ችግሩ የተከሰተው የያኔው ረሃብ እንደ 1965ቱ ረሃብ በቂ የሚዲያ ሽፋን ባለማግኘቱ ይመስለኛል፡፡

በርግጥም ያ ረሃብ ከፍተኛ እልቂት የታየበት ነበር፡፡ የንጉሡ መንግሥት የረሃቡ ወሬ ታፍኖ እንዲቀር በማድረጉ በልዮ ልዩ ክፍለ ሀገራት የሚኖረው ኢትዮጵያዊ ለትግራይ ወገኑ ሊደርስለት አልቻለም፡፡ መኳንንቱና መሳፍንቱ ከድሮም ጀምሮ የደሃው ህይወት ስለማያሳስባቸው የረሃቡን ጉዳይ ከቁብ አልቆጠሩትም፡፡ በዚያ ወቅት ድምጹን ያሰማው ብቸኛው ኢትዮጵያዊ መስፍን ወልደማሪያም ነበር፡፡

ፕሮፌሰር መስፍን የረሃቡን ወሬ የሰሙት ከተማሪዎቻቸው ነው፡፡ ረሀብ በትግራይ መኖሩ ሲነገራቸው ለንጉሡ መንግሥት ባለስጣናት አቤት አሉ፡፡ ሆኖም መንግሥቱ ለወሬው ደንታ አልነበረውም፡፡ በመሆኑም ፕሮፌሰር መስፍን የነበራቸው ብቸኛ አማራጭ ከተማሪዎቻቸው ጋር እየዞሩ ከህዝቡ እርዳታ መለመን ነው፡፡ በዚህም የተፈለገውን ያህል ውጤት ለማግኘት ባይችሉም የተወሰኑ ዜጎቻችንን ህይወት ለመታደግ በቅተዋል፡፡ በዚህም የተነሳ በወቅቱ ድምጻቸውን ያሰሙ ብቸኛው ሰው ሆነው በታሪክ ተመዝግበዋል፡፡

===የአጣሪ ኮሚሽን===

የቀዳማዊ ሃይለ ሥላሤ መንግሥት ሲንኮታኮት በርካታ ባለስልጣናት በስልጣናቸው አላግባብ በልጽገዋል በሚል ታስረው ነበር፡፡ የነዚያን ባልስጣናት ጉዳይ አይቶ ለፍርድ የሚያቀርብ አጣሪ ኮሚሽንም ተቋቁሞ ነበር፡፡ የዚያ ኮሚሽን ሊቀመንበር ፕሮፌሰር መስፍን ነበሩ፡፡

አጣሪ ኮሚሽኑ ምርመራውን በከፍተኛ ሃላፊነትና በሰከነ መንፈስ ማካሄድ ጀመረ፡፡ ይሁንና የኮሚሽኑ አካሄድ ተናዳፊዎቹን የደርግ መኮንኖች ሊያረካ አልቻለም፡፡ በመሆኑም የደርጉ ም/ሊቀመንበር የነበረው ሻለቃ መንግሥቱ ኃይለማሪያም በኮሚሽኑ ስራ ጣልቃ ገብቶ ማወክ ጀመረ፡፡ ፕሮፌሰር መስፍንንም “ቶሎ ቶሎ መታ አድርግና ጨርስ እንጂ! እስከመቼ ነው እነዚህን አሳማ ባለስልጣናት የምንቀልበው” አላቸው፡፡ ይሁንና ፕሮፌሰር መስፍን ለጓድ መንጌ ጫና አልተበገሩም፡፡ እንዲህ የሚል የድፍረት መልስ ሰጡት፡፡

“ጓድ ሊቀመንበር! የሀገር መሪ ለታሪክ ጭምር ማሰብ አለበት፡፡ ታሪክ ማለት ዛሬ ስለናንተ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ የሚጻፈው እንዳይመስልዎት፡፡ ታሪክ ጊዜው ሲደርስ እውነቱ ከሐሰቱ ተጣርቶ የሚቀረው ቅሪት ነው”

ሻለቃ መንግሥቱ በፕሮፌሰር መስፍን አነጋገር ተናደደ፡፡ ወዲያኑ አጣሪ ኮሚሽኑን በመበተን በባለስልጣናቱ ላይ የሞት እርምጃ እንዲወሰድ አደረገ፡፡

=== የብሄራዊ እርቅ ጥያቄ===

ደርግ ከሻዕቢያና ከህወሐት ጋር የሚያደርገው ጦርነት እየተጠናከረ በመጣበት ወቅት መላው የኢትዮጵያ ህዝብ በጭንቀት ውስጥ ወደቀ፡፡ ብዙዎች “ሀገራችን እንደ ሶማሊያና ላይቤሪያ ልትሆን ነው” በማለት ተወጠሩ፡፡ ይሁንና አንድም ሰው ጦርነቱን ለማስቆም ይበጃል ያለውን ሀሳብ ለመሰንዘር አልቻለም፡፡ በተለይም የጊዜው መሪ ፕሬዚዳንት መንግሥቱ ኃይለማሪያም የርሳቸውን ሃሳብ የሚጻረረውን ሁሉ ያጠፋሉ እየተባለ ይነገር ስለነበር ሁሉም ኢትዮጰያዊ በቤቱ ከትቶ ፈጣሪውን መማጸኑን ነው የመረጠው፡፡

አንድ ሰው ግን አላስቻለውም፡፡ “ሀገሬ በጦርነት አዙሪት ከምትጠፋ የመሰለኝን ሃሳብ ልሰንዝርና የሚሆነውን ልጠብቅ” በማለት የመሰለውን እርምጃ ለመውሰድ ተነሳ፡፡ “ጦርነቱን ለማቆም ብቸኛው መፍትሔ ብሄራዊ እርቅና ማድረግና የሽማግሌዎች ባለአደራ መንግሥት ማቋቋም ነው” በማለት ለፕሬዚዳንቱ ግልጽ ደብዳቤ ጻፈ፡፡ በሚቋቋመው መንግሥት አወቃቀር ላይ በሂልተን ሆቴል ማብራሪያ ሰጠ፡፡

ይሁን እንጂ ፕሬዚዳንት መንግሥቱ “የባልና የሚስት ጥል እንጂ የኢትዮጵያ ጉዳይ በሽማግሌ አይፈታም” በማለት የሰላም ፎርሙላውን አጣጣሉት፡፡ በታሪክ አጋጣሚ የተሰጣቸውን የመጨረሻ እድል አበላሹት፡፡ በመሆኑም መንጌ በወሰዱት የጀብደኝት እርምጃ ለዘልዓለሙ የታሪክ ተወቃሽ ሆነው ቀሩ፡፡ የሰላም ፎርሙላውን ያቀረበው ሰውዬ ግን በታሪክ መዝገብ ስሙን በደማቁ አስጻፈ፡፡
እንግዲህ ያ ሰውዬ ማለት ፕሮፌሰር መስፍን ወልደማሪያም ናቸው፡፡ ሰው በጠፋ እለት ሰው ሆነው የተገኙ ደፋር ሰው!!

===የለንደን ኮንፈረንስ===

በግንቦት ወር 1983 የተካሄደው የለንደን ኮንፈረንስ አዲስ የፖለቲካ አቅጣጫ ከአዲስ አዙሪት ጋር ሊያመጣ እንደሚችል ብዙዎች አስቀድመው ገምተዋል፡፡ ይሁን እንጂ የሀገሬ ጉዳይ ያገባኛል በማለት በኮንፈረሱ ቦታ የተገኘ ሰው አልነበረም፡፡ ፕሮፌሰር መስፍን ግን ስምንት ያህል ምሁራንን በማስተባበር ከኮንፈረንሱ ቦታ ሄደው ድምጻቸውን አሰምተዋል፡፡ በተለይም “የኢትዮጵያና ኤርትራ ፍቺ የሁለቱን ህዝቦች ፍላጎት ያገናዘበ ካልሆነ በስተቀር በሁለቱ ህዝቦች መካከል መቃቃርን ይፈጥራል” በማለት ቃላቸውን ሰጥተዋል፡፡ ያ አነጋገር ከሰባት ዓመታት በኋላ እውነት ሆኖ ብዙዎችን አስደንቋል፡፡

በዚያ ኮንፈረንስ ላይ በጣም አስገራሚ ሆኖ የተገኘው ሌላኛው ነገር ፕሮፌሰር መስፍን ከሻዕቢያው ኢሳያስ አፈወርቂ ጋር የነበራቸው ቆይታ ነው፡፡ ከኢሳያስ ጋር እንደ ወንድማማች ሆነው ሲጨዋወቱ ያዩዋቸው ሰዎች “ሁለቱ ሰዎች ከዚያ በፊት ይተዋወቁ ነበር እንዴ?” የሚል ጥያቄ አጭረዋል፡፡ ከአቶ ኢሳያስ ጋር ያወሩትን ያህል ከአቶ መለስ ዜናዊ ጋር አለመቀራረባቸውም ሌላኛው አስገራሚ ነገር ሆኖ ተመዝግቧል፡፡

=== የሰብዓዊ መብት ጉባኤ===

በሰኔ 1983 የተመሰረተው የሽግግር መንግሥት ያጸደቀው ቻርተር በኢትዮጵያ ውስጥ የሃሳብና የመደራጀት ነጻነት መፈቀዱን አብስሮ ነበር፡፡ በዚህም መሰረት የፖለቲካ ፓርቲዎች ከዚያ በፊት ባልታየ መልኩ እንደ አሸን ፈሉ፡፡ ህብረ ብሄራዊና ሀገር አቀፍ ፓርቲዎች ተመሰረቱ፡፡ በአንጻሩ ደግሞ “ሰብዒ መብት” የሚል ለብዙዎች እንግዳ የሆነ ጽንሰ-ሃሳብ በሚዲያ መንሸራሸር ጀመረ፡፡

አብዛኛው ምሁር ከአንዱ የፖለቲካ ቡድን ጋር ራሱን አቆላለፈ፡፡ የዘመኑ እንግዳ ደራሽ የሆነውን የሰብዓዊ መብት ጽንሰ-ሃሳብ የሚያብራራ ሰው ግን ጠፋ፡፡ በዚህ መሀል ነው ታላቁ ኢትዮጵያዊ ምሁር ብዙዎች የረሱትን የሰብዓዊ መብት አጀንዳ በማንሳት ለህዝቡ ግንዛቤ ለማስጨበጥና የሰብዓዊ መብት ጥሰቶችን በማስረጃ ለመሞገት የተነሱት፡፡ እርሳቸው ያቋቋሙት ድርጅትም ባለፉት ሀያ ሁለት ዓመታት የሰፊው የኢትዮጵያ ህዝብ ጠበቃ በመሆን ያሳለፈው ውጣ ውረድ እንዲህ በቀላሉ የሚገለጽ አይደለም፡፡

ስለ ሰብዓዊ መብትና መከራከርና በጉዳዩ ዙሪያ ግንዛቤ ማስጨበጥ በዋነኛነት በመንግሥት መፈጸም የነበረበት ስራ ነው፡፡ በመሆኑም ፕሮፌሰር መስፍን በሰሩት ስራ መንግሥት ከፍተኛ ሽልማት ሊያበረክትላቸው ይገባ ነበር፡፡ ይሁንና የተደረገው የዚህ ተቃራኒ ነው፡፡ የመንግሥት ካድሬዎች ከኢትዮጵያዊ ባህልና ስነ-ምግባር ውጪ ፕሮፌሰር መስፍንን በአጸያፊ ስድቦች ሲያብጠለጥሏቸው ነው የሰነበቱት፡፡ እርሳቸው ግን ስድቡንም ሆነ እስሩን ችለው ለህዝቡ መከራከራቸውን ቀጥለዋል፡፡ ለህዝባቸው ሲሉ ሁሉንም የተጋፈጡ ጀግና ምሁር!

===የኤርትራዊያን መባረር===

የኢትዮ-ኤርትራ ጦርነት በተከሰተበት ወቅት “የዐይናቸው ቀለም አላማረንም” የሚል ያልተለመደ ምክንያት እየተሰጠ በርካታ ኤርትራዊያን (በመቶ ሺህ የሚቆጠሩ) ተባረዋል፡፡ ታዲያ የመንግሥት እርምጃ ከተቃዋሚዎችም ሆነ ከሌሎች ወገኖች ብዙም ተቃውሞ አልገጠመውም፡፡ ፕሮፌሰር መስፍን ግን አላስቻላቸውም፡፡ “ሻዕቢያ ወረረን ተብሎ ኤርትራዊያንን በጅምላ ማባረር ታሪካዊ ስህተት መፈጸም ነው፤ ሰዎቹ ከተባረሩም እንኳ የሰብዓዊ መብታቸውን በማይነካ መልኩ መሆን አለበት” በማለት ድምጻቸውን አሰሙ፡፡ ታዲያ በዚያን ጊዜ የተፈጸመው ነገር እስከ አሁን ድረስ ለብዙዎች እንግዳ ነው፡፡ ለወትሮው ከፕሮፌሰር መስፍን ጋር በሃሳብ የሚጣጣሙት የግል ጋዜጦችም እንኳ በእርሳቸው ላይ ጀርባቸውን አዙረው የሚበቃቸውን ያህል አብጠለጠሏቸው፡፡ አንዳንዶቹ ጭራሽ ከሻዕቢያ ጉቦ የተቀበሉ አስመሰሏቸው፡፡

ጥቂት ወራት አለፉ፡፡ ኤርትራዊያንን በጅምላ ማባረር ስህተት መሆኑን ሁሉም አመነ፡፡ መንግሥት ካባረራቸው መካከል ጥቂት የማይባሉት እንደገና ወደ ኢትዮጵያ እንዲመለሱ ተደረጉ፡፡ በ1997 እንዲያውም “ኖርማላይዜሽን” የሚል እቅድ በተግባር ላይ እንዲውል ተደረገና “በጣም ድንቅ ሃሳብ” ተብሎ ተሞካሸ፡፡ ይሁንና ሁሉንም አስቀድመው የተናገሩት ፕሮፌሰር መስፍን ነበሩ፡፡ ሌሎች የርሳቸውን ሃሳብ ቀምተው ተወደሱበት፡፡ እንዲህ ነች የኛ ኢትዮጵያ!
————————
ፕሮፌሰር መስፍን ማለት በዚህች አጭር ጽሑፍ የሚገለጹ ሰው አይደሉም፡፡ ብዙ ድርሳናትን የሚያስጽፉ ታላቅ ሰው ናቸው፡፡ እኝህ ደፋርና ለህሊናቸው ታማኝ የሆኑ ምሁር በቅርቡ ሰማኒያ ሁለተኛ ዓመታቸውን ያከብራሉ፡፡ ታዲያ አንድ የሚያሳዝነኝ ነገር አለ፡፡ ብዙዎች ግለ-ታሪካቸውን እየጻፉ የህይወት ልምዳቸውን በጥቂቱ እንድንመለከት እያደረጉን ነው፡፡ በዚህ ረገድ ፕሮፌሰር መስፍን እጅግ ዘግይተዋል፡፡ የ20ኛውን ክፍለ ዘመን ኢትዮጵያን ጥልፍልፍ የታሪክ ጉዞ ሊያስተምሩን የሚችሉት ሰው ዝም ብለውናል፡፡

እነ ልደቱ አያሌውን የመሳሰሉ ትንንሽ ፖለቲከኞች እንኳ “ታሪኬን እወቁልኝ” እያሉ በሚነዘንዙበት ዘመን መስፍንን የመሰለ “አንድ ለእናቱ” የሆነ ሰው ዝም ማለቱ አግባብ አይመስለንም፡፡ ስለዚህ እኝህ የሀገር ቅርስ የሆኑ ታላቅ ሰው በቀሪው የህይወት ዘመናቸው በዚህ ላይ ሊያተኩሩ ይገባል እላለሁ፡፡
—–
አፈንዲ ሙተቂ
መጋቢት 6/2006
ሸገር -አዲስ አበባ

The writer Afendi Muteki is a reaserchr and author of the ethnography of the peoples of east Ethiopia. You may get some of his articles on the following page.
https://www.facebook.com/afendimutekiharar?ref=hl

የክርስቲያንና የሙስሊም ፍቅር በገለምሶ (አፈንዲ ሙተቂ)

0
0

ጸሓፊ፡-አፈንዲ ሙተቂ
——
gelemsoከጥቂት ሳምንታት በፊት ስለገለምሶው መምሬ ሙላቱ የምትተርክ አንዲት ጽሑፍ ለጥፌ ነበር፡፡ አሁን ሳስበው ግን ያቺ ጽሁፍ መሀል መንገድ ላይ ተቆርጣ የቀረች ሆና እየታየችኝ ነው
፡፡ ስለዚህ ለናንተም፤ ለወገንም፣ ለታሪክ ጸሓፊያንም እንዲጠቅም ይህችኛዋን ሐተታ እጨምርበት ዘንድ አስፈላጊ ሆኖ ተገኝቷል፡፡
——
በ1981 የስድስተኛ ክፍል ተማሪ እያለሁ ይመስለኛል፡፡ ከትምህርት ቤት መልስ የጨዋታ ጓዶቼን ፍለጋ “ኒብራ” ከተሰኘው የገለምሶ ከተማ ዋነኛ ጎዳና ወረድኩ፡፡ ጓዶቼን ብዙም ርቀት ሳልሄድ ከትልቁ የጋሽ መሐመድ በከር መደብር በረንዳ ላይ አገኘኋቸው፡፡ እዚያም የኳስ ጨዋታ ሰዓታችን እስኪደርስ ድረስ በትረባና በፉገራ መናቆር ጀመርንና አንዱ ሌላውን ለማብሸቅ ይሞካክር ገባ (በጊዜው ትረባ፣ ፉገራና ለከፋ ጊዜያችንን የሚገፋልን ትልቅ መዝናኛችን ነበር)፡፡ እኛ የነበርንበትን በረንዳ በስተግራ በኩል ተጎራብቶ ወደ ታላቁ የሼኽ ዑመር አሊዬ መስጊድና “ሐድራ” ወደሚባለው እስላማዊ ማዕከል (መስጊዱ የሐድራ አንድ ክፍል ነው) የሚያስወጣ መንገድ አለ፡፡ መንገዱ በወቅቱ በጎርፍ ክፉኛ ተጎድቶ ስለነበር ወደ አስር የሚደርሱ የቀን ሰራተኞች ድንጋይ እየቀጠቀጡ የተቦረቦረውን የመንገዱን የመሀለኛውን ክፍል ይሞሉትና በድንጋዩ ላይ አሸዋ እየመለሱ ይደመድሙት ነበር፡፡

ይህ የምላችሁ መንገድ በጎርፍ የተጠቃው በዚያን ጊዜ ብቻ አይደለም፡፡ ዘወትር ክረምቱን ጠብቆ ከካምቦ ተራራ በሚወርደው ሀይለኛ ጎርፍ እየተደረመሰ አሳሩን ያያል፡፡ የከተማው ማዘጋጃ ቤት በመንገዱ ዳርና ዳር የፍሳሽ መውረጃ ቢሰራለትም ጎርፉ በጣም ከባድ በመሆኑ የተሰራለትን መውረጃ በመተው ወደ መሀል መንገድ ዘው ብሎ እየገባ መንገዱን ማበላሻሸቱ የየዓመቱ ትዕይንት ነበር፡፡ በዚህም የተነሳ መኪና ይቅርና ሰዎችና የጋማ ከብቶችም በዚያ ዳገታማ መንገድ ሲወጡና ሲወርዱ መከራቸውን ነው የሚያዩት፡፡

ክረምቱ ካለፈ በኋላ መንገዱ ይጠገናል፡፡ ጥገናው የሚከናወነው በአብዛኛው በነጋዴ ግለሰቦች እንጂ በማዘጋጃ ቤቱ አይደለም፡፡ ታዲያ ከላይ በጠቀስኩትና ወሩንና ቀኑን በዘነጋሁት የ1981 አንደኛው ዕለት መንገዱን የሚያስጠግነው ግለሰብ ከወትሮው የተለየ ሆነብኝና በደንብ አየሁት፡፡

ሰውየው ቄስ ነው፡፡ መንገዱ ደግሞ ወደ መስጊድ የሚያስወጣው ትልቁ መንገድ፡፡ ቄሱ ወደ መስጊድ የሚያስወጣውን ትልቁን መንገድ ያስጠግናል!! አጃዒብ! በልጅነት አዕምሮዬ ተገረምኩ፡፡ በጣም ተደመምኩ፡፡ እናም በአቅራቢያችን የነበሩትን ጋሽ መሐመድ በከርን ስለሰውየውና ስለመንገድ ጥገናው ጠየቅኳቸው፡፡

“ዛሬ መንገዱን የሚያስጠግነው ቄስ ነው እንዴ?”
“አይ ቄሱ ሳይሆን ቤተክርስቲያን ነው”
“የቱ ቤተክርስቲያን?”
“መድኃኒ ዓለም ቤተክርስቲያን ነዋ! በገለምሶ ስንት ቤተክርስቲያን ነው ያለው?”
“ይሄ እንዴት ሊሆን ይችላል? የመስጊድን መንገድ ነው እንዴ ቤተክርስቲያን የሚያስጠግነው?”
“እንዴት ሊሆን አይችልም? እነርሱስ ቢሆኑ የኛ ሰዎች አይደሉም እንዴ? እኛስ ቤተ ክርስቲያናቸው በተፈጥሮና ሰው ሰራሽ አደጋ ቢጠቃ ዝም ብለን እናያለን እንዴ?”

ጋሽ መሐመድ የነገረኝ ነገር እውነት መሆኑን በደንብ ያረጋገጥኩት በአስር ሰዓት ገደማ ቄሱ ለሰራተኞቹ ክፍያ በፈጸሙበት ወቅት ነው፡፡ በነጋታውም እኒያ ቄስ ሰራተኞችን አሰማርተው መንገዱን ሲያስጠግኑ ነበር የዋሉት (እኚያ ቄስ የአካባቢያችን ተወላጅ አልነበሩም፤ ለዚህም ነው ስማቸውን ያልያዝኩት፡፡ ሆኖም ቀጠን ብሎ ዘለግ ያለው ሰውነታቸው፣ ጠይም መልካቸውና ሰልካካ አፍንጫቸው እስከ አሁን ድረስ ይታወሱኛል፤ ብዙ ጊዜም ሰማያዊ ቀለም ያለው ቆብ ነው በራሳቸው ላይ የሚያደርጉት)፡፡

ልብ ያለው ይበል! እንዲህ አይነት ታሪክ በገለምሶ ተፈጽሟል፡፡ የገለምሶ መድኃኒዓለም ቤተክርስቲያን ወደ ሼኽ ዑመር አሊዬ መስጊድ የሚያስወጣውን መንገድ በራሷ ገንዘብ አስጠግናለች፡፡ በገለምሶ የክርስቲያንና ሙስሊሙ ፍቅር እስከዚህ ድረስ ነበር፡፡ ዛሬ በአካል እዚያ ባልኖርም ይህ የጥንት ፍቅራችን አሁንም ድረስ እንዳልቀዘቀዘ ቤተሰቦቼ ያወጉኛል፡፡
***** ***** *****
“የሼኽ ዑመር አሊዬ መስጊድስ ለክርስቲያኖችና ለቤተክርስቲያኒቷ ምን አድርጎ ያውቃል?” ብላችሁ መጠየቃችሁ አይቀርም መቼስ! እንዲያ ከሆነ የሚከተለውን ታሪክ ላጋራችሁ፡፡

የሼኽ ዑመር አሊዬ መስጊድ “ሐድራ” የሚባለው እስላማዊ ማዕከል አንዱ ክፍል ነው- ከላይ እንደጠቀስኩት፡፡ ይህ ሐድራ የሚባለው ማዕከል ከትልቁ መስጊድ ሌላ የቁርአን መማሪያ (ቁርአን ጌይ)፣ የዒልሚ መማሪያ (ቤይተል ዒልሚ)፣ የሴቶች መማሪያና መስገጃ፣ የዚክሪና አውራድ ማድረጊያ፣ የአዛውንቶችና የሽማግሌዎች መኖሪያና ሌሎች በርካታ ቤቶች አሉት፡፡ እንዲሁም “ቤይቱል ሐድራ” የሚባለውና የሁሉም እንግዶች ማረፊያ የሆነው ቤት (በስፋቱ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲውን ልደት አዳራሽ የሚያክል) በዚሁ ሐድራ ውስጥ ነው የሚገኘው፡፡ እነዚህ ቤቶች ሁሉ ከዓመት እስከ ዓመት ተመሳሳይ አገልግሎት ነው የሚሰጡት፡፡ በመውሊድ ጊዜ ግን አገልግሎታቸው ይቋረጥና በበዓሉ ለመታደም የሚመጡትን እንግዶች ያስተናግዳሉ፡፡ በየቤቶቹ ውስጥ ሰለዋትና መንዙማ ይደረጋል፡፡

በገለምሶ የሚከበረው መውሊድ ሞቅ ደመቅ ያለ ነው፡፡ በበዓሉ ላይ የሚታደሙ እንግዶች ከሁሉም የኢትዮጵያ ክፍለሀገራት ይመጣሉ፡፡ ከዚህም አልፎ ከጎረቤት ሀገራት ጭምር (ሶማሊያ፣ ጅቡቲ እና የመን) በርካታ ሰዎች ይመጣሉ፡፡ እነዚህን እንግዶች ለማስተናገድ በትንሹ አስራ አምስት በሬዎችና ሶስት ግመሎች ይታረዳሉ፡፡ ግመሎችና በሬዎቹን የሚገዙት ግን የሐድራው ሰዎች አይደሉም፡፡ ድሮ በሼኽ ዑመር አሊዬ እጅ የተማሩ ሼኮችና ሌሎች የሼኽ ዑመር ወዳጆች ናቸው ከብቶቹን የሚያመጡት፡፡

ታዲያ የሐድራው ሀላፊዎችና የመስተንግዶ መሪዎች ወደነርሱ የሚመጡትን ከብቶች በሙሉ አያርዷቸውም፡፡ በቅድሚያ አንድ ወይም ሁለት በሬ ለሴቶች ይሰጥና የከተማው ሴቶች ከልዩ ልዩ ክፍለ ሀገራት የሚመጡ ወይዛዝርትን እንዲያስተናግዱበት ይደረጋል (በሐድራ ውስጥ ሴትና ወንድ መቀላቀል ክልክል ነው፤ ሴቶችም ሆኑ ወንዶች ምግባቸውን ለየራሳቸው ነው የሚያዘጋጁት፤ ደግሞም የሁለቱም ጾታ ሰዎች ከተፈቀደላቸው ክልል ውጪ መውጣት የለባቸውም)፡፡

በማስከተልም አንድ በሬ ለስጋ ደዌ በሽታ ተጠቂዎች ይሰጣል፡፡ እንዲህ የሚደረግበትን ምክንያት በትክክል ባላውቅም በዘመኑ በነበረው ልማድ የተነሳ የበሽታው ተጠቂዎች መሸማቀቅ ሳይደርስባቸው ራሳቸውን በራሳቸው እንዲያስተናግዱ ማድረጉ አስፈላጊ ሆኖ ስለተገኘ ይመስለኛል፡፡ በሬዎቹ ለሴቶችና ለስጋ ደዌ ህሙማኑ የሚላኩት ግን ለግብዣና ለፌሽታ ብቻ አይደለም፡፡ በመስተንግዶው የሚታደሙት ሰዎች ሰለዋት ስለሚያደርጉና የነቢዩን ገድል በመንዙማ ስለሚያወድሱ ነው፡፡ እንዲያ የማያደርግ ጀመዓ ለመውሊድ ከመጣው በሬ አንዳች ድርሻ የለውም፡፡

ነገር ግን ይህ መመሪያ የማይመለከተው አንድ ክፍል አለ፡፡ የገለምሶ መድኃኒዓለም ቤተክርስቲያን! በዓሉን የማታከብር ሆኖም ከመውሊድ በሬዎች የራሷ ድርሻ የነበራት ብቸኛ አካል እርሷ ነበረች፡፡ ለዚያውም ለርሷ የሚደርሳት አንድ በሬ ብቻ አይምሰላችሁ! ሁለት በሬዎችን ነው በየዓመቱ የምታገኘው፡፡

የዚህ ምክንያት ለረጅም ጊዜ ሊገባኝ አልቻለም፡፡ ዕድሜዬ ከፍ ካለ በኋላ ግን ምክንያቱን የሐድራው መሪ የሆኑትን ሼኽ ሙሐመድ ሲራጅን ጠይቄ ከአንደበታቸው ተረዳሁ (ሼኽ ሙሐመድ ሲራጅ የሐድራው መስራች የነበሩት የሼኽ ዑመር አሊዬ ልጅ ናቸው- አሁን ዕድሜአቸው ከዘጠናው ተሻግሮ ወደ መቶ ዓመት እየተጠጋ ነው)፡፡

ሼኽ ሙሐመድ ሲራጅ ሁለት በሬዎች በየዓመቱ ለቤተክርስቲያን የሚሰጥበትን ምክንያት እንዲህ በማለት ነበር ያስረዱኝ፡፡

“እነዚህ ክርስቲያኖች ወንድሞቻችን ናቸው፡፡ እንደኛው የአዳም ልጆች ናቸው፡፡ በሀይማኖት ብንለያይም የአንድ ሀገር ሰዎች ነን፡፡ ከዚያም አልፎ የአንድ ከተማ ነዋሪዎች ነን፡፡ በሬዎቹ ወደኛ የሚመጡት በዓላችንን በደስታ ለማክበር እንድንችል ነው፡፡ እኛ በሬዎቹን አርደን በዓላችንን በደስታ ስናከብር ክርስቲያን ወገኖቻችንን መዘንጋት የለብንም፡፡ እስልምናችን ጎረቤቶቻችንንም ማስደሰት እንዳለብን ያዘናል፡፡ ስለዚህም ነው በሬዎቹን ወደ ቤተክርስቲያን የምንልከው”፡፡
***** ***** *****
እንዲህ ዓይነቱን ውብ ባህል ምንድነው የምትሉት? “መቻቻል” ነው የሚባለው ወይስ ሌላ ስም አለው? እኔ ግን “መቻቻል” አልለውም፡፡ ይህ በተመን የማይመነዘር ፍቅር ነው እንጂ “መቻቻል” የሚለው ዘመን ወለድ ታፔላ የሚለጠፍለት አይሆንም፡፡ “መቻቻል” ሲባል አንዱ ወገን በማወቅም ሆነ ባለማወቅ ሌላውን የሚያስከፋ ድርጊት በሚፈጽምበት ጊዜ ሌላኛው ወገን በትዕግስት ችሎ ማለፍ ይገባዋል የሚል እድምታ ያለው ይመስለኛል፡፡ በኔ ከተማ ግን ፍቅር ሰባኪ የሆኑት ሼኮች እና ቄሶች ክፋት ሊፈጸም የሚችልባቸውን ሽንቁሮች ሁሉ ቀድመው የደፈኗቸው በመሆኑ “መቻቻል” የሚባለው አነጋገር እዚያ ዘንድ ተራ ጉዳይ ነው የሚሆነው፡፡ በዚያች እትብቴ በተቀበረባት መሬት ያየሁትና የሰማሁት “ፍቅር” ነው እንጂ “መቻቻል” አልነበረም፡፡

በኔዋ የገለምሶ ከተማ እንዲህ ዓይነት ፍቅር ነበረን፡፡ በሌላው ኢትዮጵያስ ቢሆን? ዲግሪው (መጠኑ) ይለያይ ይሆናል እንጂ ተመሳሳይ ታሪኮች ሞልተዋል፡፡ እንዲህ በህብረት የኖረውንና ፍቅርን የተቋደሰውን ህዝብ የፖለቲከኞች ወሬ ሆድና ጀርባ ሊያደርገው ከቶ አይቻለውም፡፡ ፖለቲከኞች ይህንን በሌሎች ሀገራት በስለት እንኳ ተፈልጎ የማይገኝ ውብ ባህላችንን በዓለም ዙሪያ ቢያስተዋውቁልን ነው የሚያምርባቸው፡፡

እኛ አንድ ነን፡፡ ወንድማማቾች ነን፡፡ ፍቅር ነን፡፡ ክብር ነን፡፡ ህብር ነን፡፡ ሰሞነኛ ወሬ አያለያየንም፡፡
—–
አፈንዲ ሙተቂ
ነሐሴ 21/2005

ጃኪ ጎሲ ተሾመ አሰግድን ይቅርታ ጠየቀ

0
0

jacky teshome
በApril 24, 2012 ዓ.ም የዘ-ሐበሻ ጋዜጣ ዕትም ላይ ዝነኛው ድምጻዊ ተሾመ አሰግድ “በጠራራ ጸሐይ ተዘረፍኩ፤ የኢትዮጵያ ሕዝብ ይፍረደኝ” ሲል ድምጻዊ ጎሳዬ ቀለሙ (ጃኪ ጎሲ) ካለፈቃዴ “የኔ አካል” የሚለውን ተወዳጅ ዘፈኔን ወስዶ ተጫውቷል በተቃውሞ ነበር። ከጊዜ በኋላ ድምጻዊ ጃኪ ጎሲ በጆሲ ሾው ላይ በመቅረብ “ከዚህ በኋላ ተሾመ ይህን ዘፈን የኔ ነው ብሎ መጠየቅ አይችልም፤ ለዜማና ግጥም ደራሲዎቹ ከፍዬበታለሁ” ሲል ተናግሮ እንደነበርም ይታወሳል።

ጃኪ ወደ ሰሜን አሜሪካ ሲመጣ ይታየው የተባሉ ጸሐፊ “ድምጻዊ ጎሳዬ ቀለሙ (ጃኪ ጎሲ) ከተሾመ አሰግድ ለወሰደው ዘፈን ይቅርታ ይጠይቅ ይሆን? ወይስ ማን አለብኝነት ያልፈዋል?” ሲሉ ተሾመ ከዚህ ቀደም የሰጠውን ቃለምልልስ በመጥቀስ አስተያየት ጽፈው ነበር። ወደ ኢትዮጵያ ሙዚቃ ኮከብነት እየተጓዘ የሚገኘው ጃኪ ይህን አስተያየት በብልህነት የተመለከተው ይመስላል። በዚህም መሠረት ትናንት በዋሽንግተን ዲሲ ባደረገው የመጀመሪያው የሰሜን አሜሪካ ኮንሰርቱ ላይ ሰው ባልጠበቀው ሁኔታ ዝነኛውን ድምጻዊ ወደ መድረክ በማምጣት አብሮት “የኔአካል” የሚለውን ተወዳጅ ዘፈን ካቀነቀኑ በኋላ ድምጻዊ ጃኪም ካለፍቃዱው ወስዶ በመስራቱ ይቅርታ ጠይቋል። ጨምሮም ዘፈኑን የሰራው ከመውደዱ የተነሳ እንደሆነ ገልጿል። አርቲስት ተሾመ አሰግድም “እዚህ ሃገር ሰንመጣ መንገዱን ያሳየን ሰው አልነበረም። ጥረታችን የቀድሞ ሙዚቃኞቻችን ውለታ እንዲህ በቀላል እንዳይረሳ ሙዚቃዎቹን ስትጫወቱ በፈቃድ ጥያቄ ጠይቃችሁ ተጫወቱ። [የኔ አካል] ከኔ በበለጠ ጃኪ ተጫውቶታል። አብልጦ ነው የተጫወተው፤ ሞቅ አድርጉለት” ብሎ አርቲስቱም ይቅርታውን ተቀብሏል። ጃኪም የሕዝብ ድምጽን ማድመጡ፤ ከምንም በላይ ይህን ስመጥር አርቲስት በመድረክ ጋብዞ እንዲታወስ በማድረጉ ዘ-ሐበሻ አድናቆቷን በዚህ አጋጣሚ እየገለጸች፤ አንባቢዎች በዘ-ሐበሻ የተጀመረው የጃኪና የተሾመ ጉዳይ መቋጨቱን በዚህ አጋጣሚ እንገልጻለን። መልካም የሥራ ዘመን ለሁለቱም።
የይቅርታውን ስነስርዓት ቪዲዮ ይመልከቱ

የግርጌ ማስታወሻ ጥቂት ስለስመጥሩ አርቲስት ተሾመ አሰግድ፦
በኢትዮጵያ ስመ-ጥር ከሆኑ ድምጻዊያን መካከል የሆነውና ብዙዎች “ኢትዮጵያዊው ስቲቭ ዎንደር” የሚሉት ተሾመ አሰግድ በኢትዮጵያ አቆጣጠር በመስከረም ወር 1945 ተወልዶ በተወለደ በ5 ወሬ ዓይነ ስውር መሆኑን በዘ-ሐበሻ ጋዜጣ ቁጥር 2 ላይ በሰጠው ቃለ ምልልስ መናገሩ ይታወሳል። የመጨረሻ ካሴቱን ካወጣ 17 ዓመት ያለፈው ይህ ድምጻዊ እስካሁን ስንት ካሴቶችን ሰርተሃል በሚል ጥያቄ አቅርበንለት “ጥቂት ካሴቶችን አውጥቻለው:: ትዝታና ባቲ በሚባለው የሙዚቃ ቅኝት በፊሊፕስ አሳታሚነት በ1960ዎቹ አንድ ሸክላ አውጥቼ ነበር:: ከዛ በተረፈ ያልተሳካለት አንድ ካሴት ሰርቼ ነበር:: ከዛ ወዲህ ግን ጅቡቲ ለ5 አመታት ከቆየው በሗላ ከሮሀ ባንድ ጋር በመሆን ‘የኩባያ ወተት”ን ሰራሁኝ:: ይበልጥ ከሕዝብ ጋር ያስተዋወቀኝም ይሄ ሥራ ነው:: በሌላ በኩል ከነራሄል ዮሐንስ; አሰፉ ደባልቄ እና ኬኔዲ መንገሻ ጋር አንድ ካሴት; እንዲሁም ከማርታ አሻጋሪ; በዛወርቅ አስፋው እና ኤልያስ ተባባል ጋር በመሆን አንድ ኮሌክሽን ሰርቼ ነበር:: በራሴ በኩል 2ኛውን ሙሉ ካሴቴን “ደርባባዬ’ን አውጥቼ ነበር:: ብዙም በሕዝብ ዘንድ አልገባም:: ግን አልፎ አልፎ ሰዎች ያውቁታል::” ሲል መልሷል።

መንግስት በደቡብ ጉራጌ ዞን ከእምድብር ከተማ ወጣቶች ጋር በስተርጅና “ሌባና ፖሊስ”ጨዋታ እየተጫወተ ይገኛል

0
0

በደቡብ ክልል በጉራጌ ዞን ቸሃ ወረዳ እምድብር ከተማ ላይ የፋሲካ ማግስት ማታ የደቡብ ክልል ልዩ ሀይሎች ከከተማው ወጣቶች ጋር ግጭት ውስጥ ገቡ።
Gurage Kilele
በፋሲካ ማግስት አምሽተው ወደ ቤታቸው በመግባት ላይ ከነበሩ ወጣቶች ከወልቂጤ—ሆሳዕና መንገድ የመልሶ ግንባታ በማካሄድ ላይ የሚገኘውን የCGGC ካምፓኒ ንብረት ለመጠበቅ ከተመደቡ የደቡብ ክልል ልዩ የፖሊስ ሀይሎች ጋር በተፈጠረ አለመግባባት ፖሊሶቹ ወጣቶቹን መደብደብ ሲጀምሩ ወጣቶቹ ባሰሙ የይድረሱልኝ ጩኸት የከተማው ሰው በብዛት በመውጣት ለማረጋጋት ሲሞክር ፖሊሶቹ ተኩስ በመክፈት እስከ 12 ጥይት የተኮሱ ቢሆንም በተኩሱ የተጎዳም ሆነ የሞተ ሰው የለም።

ፖሊስ ለምን ይህን እርምጃ እንደወሰደ ሲጠየቅ “በጥበቃ ላይ በነበርንበት ወጠቶቹ መጥተው ድንጋይ ወረወሩብን” በማለን ምክንያታቸውን ሲገልጹ ወጣቶቹ በበኩላቸው ይህ ሆን ብሎ የተቀነባበረና የአካባቢው ወጣቶች ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ከመንገዱ ጋር ተያያዥዥ የሆኑና ሌሎች ልማታዊ መብቶችን በመጠየቃችን የወረዳው አመራሮች በማቄማቸው እና ይህን የመብት ጥያቄ በማጠልሸን የጥያቄዎቻችንን መልክ ማስለወጥ በመፈለጋቸው የተሸረበ ሴራ ነው በማለት ሲገልፁ በአካባቢውም የነበሩ የአይን እማኞች አንድ ማንነቱ ያለኙት ወጣት ከአንድ ሹፌር ጋር ተጣልቶ ለሱ የወረወረው ድንጋይ ወደ ፖሊሶቹ አልፎ ድንጋዩ ሳይገባ እዳልቀረ ግምታቸውን ያስቀምጣሉ።በማያያዝም በወቅቱ ድለኘንጋይ ወርዋሪው ሮጦ ሲያመልጥ በወቅቱ በመንገዱ ሲያልፉ የነበሩ ልጆችን ይዘው ሲደበድቡ ድንጋይ ተወረወረበት የተባለው ሹፌር ወደ ፖሊሶች በመምጣት ወርዋሪው ጓደኛው እንደሆነና ድንጋዩንም የወረወረው እየተቀላለዱ እንደነበበር ሲገልፅላቸው እንደሰሙ አክለው ገልፀዋል።

በአሁን ሰዓት 4 የከተማው ወጣቶች በዕለቱ ተይዘው ወልቂጤ ከተማ እሚገኘው አበሽጌ ወረዳ ፖሊስ ጣቢያ የተወሰዱ ሲሆን በወቅቱ ግርግሩ ሲፈጠር በቦታው ያልነበሩ ወጣቶችን ፖሊስ ለመያዝ እንቅስቃሴ ሲያደርግ መረጃው ቀድሞ የደረሳቸው ወጣቶች ከተማዋን ትተው በመውጣት ለስደት ተዳርገዋል።

በወረዳዋ እጅግ ዘርፈ ብዙ አስተዳደራዊ ችግሮች እንዳሉ የወረዳዋ ነዋሪዎች በተደጋጋሚ ሲገልፁ ይደመጣሉ።ከነዚህም ውስጥ በተለያየ ጊዜ በሚሾሙ ባለስልጣናት የተመዘበረው ከግብአት ገቢ መሆን ያለበት ከ3.4 ሚሊየን ብር በላይ በመመዝበሩ ወረዳዋ ባለ ዕዳ በመሆኗ የመንግስት ሰራተኞች ከሌላው ወረዳ በተለየ ከ10—20 ቀናት ዘግይተው ደሞዝ እንደ ሚወስዱና ይህን ተከትሎ እጅግ ብዙ ሰራተኞች እንደሚፈልሱ ይታወቃል።

አገር እንዲህ ኾናም አትቀርም (በጽዮን ግርማ)

ምርጫ መጣ፤ ምን ይመጣ ይሆን? (ታክሎ ተሾመ)

0
0

2007 election

 

መቼም ምርጫ ሲነሳ ብዙ ትዝታዎች መኖራቸው አይቀሬ ነው። በዚህች ምድር ከግለሰብ እስከ ማኅበረሰብ ድረስ ጐጅና ጠቃሜ የሆኑ  ብዙ ውጣ ውረዶች ይስተናገዳሉ። ሁሉም እንደየስሜቱ  ክፉና ደጉን የመለየት ባህሪ አለው።  ምርጫ ማለት  ከሁለት ነገሮች አንዱን መምረጥ ማለት ይመስለኛል። አንድ ሰው ምግብና መጠጥ ሊመረጥ ይችላል። የወደፊት ፍቀረኛውን ሊመርጥ ይችላል፤ ሥራም ሊመርጥ ይችላል፤ የሚኖርበትን አገር ይመርጣል። ስለዚህ ምርጫ ሲባል ብዙ ነገሮችን  ይመለከታል።

 

ከላይ ይኽን ካልኩ ዘንዳ  ሕዝብ  ምርጫ  ለምን አስፈለገው  የሚለውን  በመጠኑ  መዳሰስ አስፈላጊ ነው። ሰው የሚለው ሥም  ጥቁር ቆዳ፤ ነጭና ቢጫ ቆዳ፤ የቀይ ዳማ ቆዳ  የሚመስል  መልክ አለው። በዚህ ሁኔታ ሰው የቆዳ  ልዩነት አለው። እንዲሁም ሰው የእምነት፤ የቋንቋ፤ የአመለካከት ልዩነት አለው። ነገር ግን ሰው የሚለው ሥም አንድ በመሆኑ የቆዳ ልዩነት ይታይበት  እንጂ  በሰብአዊ  መብት ዙሪያ ግን ሁሉም እኩል መብት ሊኖረው እንደሚገባ  መጠራጠር  አይቻልም።

 

ከኅብረተሰብ እስከ ግለሰብ የሚደርስ  ሰብአዊ መብቶቹን የሚደነግግ በተባበሩት መንግሥታት ዘንድ  በሕገ- የጸደቀ  መሆኑ አይታበልም። ሰዎች በፈለጉት መንግሥት መተዳደር  እንደሚችሉ ሕገ መንግሥቱ ያዛል። አገራዊ ምርጫ  ሲደረግ  ለአገርና ለሕዝብ  ሊጠቀም  የሚችል  ፓርቲ  ይመረጣል። ነገር ግን  ተግባርና አዋጅ ሥራቸው እየቅል እንዲሉ በአፍሪካ ነፃ ምርጫ  ብሎ ነገር የለም። ቢሆንም ምርጫው ፍትሃዊ ሆነም አልሆነ  የምርጫ  ሰዓት  ሲደርስ  እያንዳንዱ የሚመቸውን የመምረጥ መብት  ያለው  ይመስለኛል።

 

የሰው ልጅ ግን ከእንሰሳት በተሻለ ሁኔታ የማሰብ ችሎታው ከፍተኛ በመሆኑ መብቱን ከሚጨቁኑት፤ ከሚያስርቡት፤ ከሚያስሩት፤ ከሚገድሉትና ከሚያሰድዱት ጋር የሞት የሽረት ትግል እያደረገ ማንነቱን ያረጋግጣል። በአገራችን ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ባለመኖሩ ሰብአዊ መብቶች አልተከበሩም። ከአጼው እስከ ደርግ ድረስ የነበሩ የፍትህ-ሥርዓቶች የአገር ደህንነትን የተጠበቁ ቢሆንም ሕዝቡን ክፉኛ ያጐሳቆሉ ሥርዓቶች እንደነበሩ አይዘነጋም። ዛሬም ቢሆን ኢሕአዴግ በመጀመሪያዎች ዓመታት ብልጪ አድርጓቸው የነበሩትን የዴሞክራሲ ፍንጮች መልሶ አዳፍኗቸዋል።

 

በኢትዮጵያ በየአምስት ዓመቱ አገራዊ ምርጫ ቢደረግም የፖለቲካው ድብብቆሽ ግን አሁንም እንደቀጠለ ነው። ድብብቆሹ በመንግሥት ብቻ ሳይሆን የፖለቲካ ድርጅቶችንም ይመለከታቸዋል። ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ኖረም አልኖረ መንግሥትና የፖለቲካ ድርጅቶች ምን ጊዜም ይኖራሉ። ነገር ግን ልዩነቶቻቸውን ለአገርና ለሕዝብ ሲሉ አቻችለው መሄድ የማይችሉ ከሆነ የሰው ሕይወትና የአገር ንብረት መውደሙ አይቀሬ ነው። በአገራችን እስከ ዛሬ ድረስ እየታየ ያለው ይህ  እውነታ  ነው።

 

ከላይ ይህን ካልኩ ዘንዳ ከዚህ በፊት በአገራችን የተካሄዱትን አገራዊ ምርጫዎች ምን ይመስሉ እንደነበር መዳሰስ አፈላጊነው። ቢሆንም ሁነቶች ፍትው ብለው ስለሚታወቁ ባለፈ ነገር  ጊዜ ማባከ ትክክል መስሎ ስላልታየኝ ቀጣዩ የ2007 ዓ.ም ብሄራዊ ምርጫ ምን ሊሆን ይችላል የሚለውን በመጠኑ ማንሳት ይበጃል። የ2007 ዓ.ም ብሔራዊ  ምርጫ  በምን  መልክ  ይከናወን  ይሆን?  ፓርቲዎችስ ለዚህ ተዘጋጅተዋል ወይ? ሕዝቡስ ምን ሊያደርግ  አስቧል? መንግሥትስ  ቀጣዩን ምርጫ ፍትሃዊ ለማድረግ  ምን  አስቧል? የሚለው ቀጣይ  አጀንዳ ሆኖ ሁሉም ሊያስብበትና ሊመክርበት ይገባል። በየጊዜው የተደረጉ ምርጫዎች አስመሳይ መሆናቸው እርግጥ ነው። ምክኒያቱም መንግሥት ሥልጣኑን  ለሕዝብ  ለማስረገብ እየተቸገረ በሕገ-መንግሥት ያስቀመጣቸውን ሕግጋት ተግባር ላይ ለማዋል  አልደፍረምና።

 

ሙሽራ መጣ ቄጠማ እንዲሉ ፓርቲዎችም ቢሆኑ ምርጫ መጣ ሲባል ካልሆነ በስተቀር  አስቀድመው ሲዘጋጁ አይስተዋሉም። አንድ የፖለቲካ ድርጅት መሪ  ትግሉን እመራለሁ ከማለቱ በፊት ከራሱ ባሕሪ ጋር መጀመሪያ ሙግት መግጠም አለበት። ሙግቱ ትግሉን ለመምራት ብቃቱን፤ ጥንካሬውን፤ መስዋዕት ለመሆኑ ቁርጠነቱን፤ ከግል ዝና መጽዳቱን፤ እውነተኛ  ለሕዝብና ዴሞክራሲ  የቆመ ስለመሆኑ ከሕሊናው ጋር ሙግት መግጠብ አለበት። ከዚህ በተጨማሪ የነደፈው ፕሮግራም ምን ያህል ለአገርና ለሕዝብ ይጠቅማል? ሕዝቡስ ፕሮግራሙን ተቀብሎ  መሰረታዊ ሥር-ነቀል ለውጥ እስኪመጣ ድረስ  ከፓርቲው ጋር ይወግናል ወይ? ፓርቲው ከሰርጐ ገቦች የጸዳ መሆኑን  ወዘተ  ሊሟሉ የሚገባቸውን ነገሮች ቅድሚያ አስቀድሞ ማጤን ያስፈልጋል። ነገር ግን በይሁን ይሁን  የመሪነት ሥም በመያዝ ለምርጫ መቅረብ  መሰረታዊ ለውጥ ሊያስገኝ አይችልም።

 

ምርጫው የተወሳሰበና ከአስመሳይነት ሊወጣ ያልቻለበትን  ምክኒያት ብዙ ነው።  ፍትሃዊ ምርጫ እንዳይካሄድ  መንግሥት የሚያደርገው ጫና ቀላል  አይደለም።  ከዚህ በፊት ተደጋግሞ እንደታየው መራጩ ሕዝብ  ነፃ ሆኖ የሚበጀውን እንዳይመርጥ መንሥግስት በግልጽና በጃዙር የሚያደርገው ተጽኖ አስከፊ መሆኑ አይካድም። ፓርቲዎች  ከሕዝባቸው ጋር በየጊዜው እንዳይወያዩ ነፃ ሚያዎችን ገዥው ፓርቲ ያፍናል። በመሆኑም በሚዲያ እጥረት ፓርቲዎች ሕዝቡን ከጫፍ እስከ መሃል መቅረብ  ይቸገራሉ።  የምርጫ አስፈፃሚው አካል ገለልተኛ ባለመሆኑ ተቃዋሚዎች ቢያሸንፉ እንኳን ምርጫ ቦርዱ ተሟሙቶ የድምጽ መስጫ  ሳጥኑ ተገልብጦ ወደ ገዥው ፓርቲ  የድምጽ መስጫ ሳጥን  እንዲገባ  ያደርጋል። ይህ ድርጊት  በተግባር የታየ  ሰለሆነ  ወደፊትም  እኩይ  ተግባሩ  ሊቀጥልበት  እንደሚችል  እገምታለሁ።

 

ባንፃሩ የፖለቲካ ድርጅቶች ድክመት የለባቸውም ማለት አይቻልም። ምርጫ ሲነሳ ከብዙ ስዎች ጋር ያገነጋግራል። የአገራችን  ፖለቲካ  ድርጅቶች  ምን  ሊመስሉ እንደሚችሉ ከአገር ቤት አንድ ወዳጀ  እንዲህ ሲል ገልጾታል። ” በእኔ ግምትና  እምነት በአሁኑ ወቅት በአገራችን ባሉ የፖለቲካ ፓርቲዎች ላይ ሕዝቡ ሥር የሰደደ ጥላቻ  ባይኖረው  ደካማነታቸውን  ተቀብሎ  ተስፋ   ቆርጦባቸዋል።  ኢሕአዴግ ሕዝቡን  በማስገደድም ሆነ  በጥቅማጥቅም  በመያዙ  በእያንዳንዱ  ንቁጣ  መንደር ሁሉ ስለገባ ዙሪያ ገባው  ጨለማ  መስሎአቸው ፓርቲዎች ሕዝቡንም መፍራትና መጠራጠር  የጀመሩ ይመስላል።

 

ፓርቲዎች ለክፉ ቀን የሚሆን የረባና ጠንካራ መዋቅር የላቸውም። እንቅስቃሴያቸ ሁሉ ለሕልውና ያህል የሚደረግ መፍጨርጨር ሲሆን ብዙዎች ጊዜያቸውን የሚያባክኑት በውስጥ ጉዳይ በመሻኮትና ሌሎች ድርጅቶችን ጠልፎ ለመጣል  በመሮጥ ነው።” ከዚህ ሌላ የመንግሥት ችግር እንዳለ ሆኖ  የአገራችን ፖለቲካ ችግሩ  ውስብስብ ሊሆን  የቻለው  አብዛኛው  ቡድናዊ  ይዘት ሲኖረው እኔ ብቻ አውቅልሃለሁ ሌላው ይከተል፤ ሃሳብ አይስጥ፤ እኔ ከመሪነት ከወረድኩ ትግሉ የደረቀ ሣር  ይሁን ባዮች በመብዛታቸው ነው። ይሁን እንጂ  አገር ቤት ውስጥ የሚቀሳቀሱ ድርጅቶች ይብዛም ይነስ ሊመሰገኑ ይገባቸዋል። ነገር ግን በውጭ  የሚገኙ የፖለቲካ ፓርቲዎች በነፃ አገር በነፃነት መንቀሳቀስ እየቻሉ  በስሜት ብቻ መወሰናቸው አስገራሚ ነው። ይባስ ብለው  አንዳንዶች ወደ  ዘር  ፖለቲካ  የወረዱ  አሉ።

 

በኢትዮጵያ ተደጋጋሚ ምርጫዎች ተካሂደዋል። በየጊዜው አሸንፊያለሁ የሚለው ገዥው ፓርቲ ነው። ተቃዋሚዎች ለምን የማሸነፍ እድል አላጋጠማቸውም ብለን ብንጠይቅ  የሚሰጡን መልስ  መንግሥት  ሳጥን ገልብጦ  ውጤታችን  ስለቀማን  ነው  ይላሉ። ይህ  እውነት እንዳለ ሆኖ ግን ተቃዋሚዎች የአገሪቱን ተጨባጭ ሆኔታ ተገንዝበው በጋራ መቆም  ባይችሉም  የየራሳቸውን  ፕሮግራም  ይዘው አንዱ ሌላውን ድርጅት  ሳይተነኩስ  በያሉበት ተቻችለው  ሕዝቡን አሰባስበው ለምርጫ  ማቅረብ አልቻሉም።

 

ለመጀመሪያ ጊዜ የኢትዮጵያ ሕዝብ በነቂስ ወጥቶ ለምርጫ የተሳተፈበት ጊዜ  ቢኖር ግንቦት 7 ቀን 1997 ዓ.ም በተካሄደው አገራዊ ምርጫ ላይ ነው። የግንቦቱ 7 1997 ዓ.ም አገራዊ መርጫ ተካሂዶ በነበረበት ወቅት ተቃዋሚዎች የሕዝብ ድምጽ ማግኘታቸው  አይታበልም። ነገር ግን ያን ድምጽ ሊያገኙ የቻሉት ጥንካሬ ኖሮቸውና ሕዝብ  አምኖባቸው ሳይሆን አማራጭ  በማጣት እንደነበር  ብዙዎች  ይስማሙበታል። ቅንጅት ውስጥ የተሰባሰቡ ቀስተዳመና እዴፓ መኢአድ እውነት ልብ ለልብ ተገናኝተው ነበር ወይ? እውነት ለመስዋዕትነት ተዘጋጅተው  ነበር  ወይ?  እውነት 15 ቱ  አድርጅቶች  በኅብረት  የተሰባሰቡት ከልባቸው ነበር ወይ? ብለን ስንጠይቅ ከማስመሰያነት ውጭ በእውነት ላይ የተመሰረተ ግንኙነት እንዳልነበራቸው ብዙ የሚያመላክቱ ሁነቶች ነበሩ።

 

የኢደፓ ሊቀመንበር  የነበሩት አቶ ልደቱ አያሌው በሚፈጥሩ የማስመሰያ ቃላት በቅንጅት ውስጥ የሚደረጉ ስብሰባዎች የአንዳንዶችን ስሜት ማሻከሩ አልቀረም።  እንደምናስታውሰው በቅንጅት ውስጥ በተፈጠረው የእርስ በርስ ጥርጣሬ የቅንጅት ምስጢሮች እየሾለኩ ከመንግስት ጀሮ ይደርሱ ነበር። ፓርላ መግባት፤ አለመግባት የለም የተሰረቀውን ድምጽ ማስመለስ አለብን በሚለው ዙሪያ  ከቅንጅ ሰርገው የገቡ ሰዎች አመራሩን ውዥንብር  ፈጠሩበት። የመጣው ይምጣ የሕዝብ ድምጽ ተሰርቆ ፓርላማ አንገባም ብለው  በአቋማቸው የጸኑ አመራር አባላት ታሰሩ፤ ተንገላቱ፤ ቤተሰቦቻቸው ሳይቀሩ ችግር ላይ ወደቁ።

 

በዚህ ጊዜ ድምጽ ሰጥቶ የመረጣቸው ሕዝብ ከሞላ ጐደል የታሰሩትን ለማስፈታት ከጫፍ እስከ መሀል አገር ሕዝቡ ሆ ብሎ ሊነሳ አልቻለም። ዲያስፖራው ግን  ሰላማዊ ሰልፍ  በማድረግ በሃሳብ ከጐናቸው  እንደነበር አይዘነጋም። ለታሰሩ የቅንጅት አመራር አባላት ቤተሰቦች የተቻለውን ያህል የገንዘብ ድጐማ ማድረጉን አስታውሳለሁ። በጨረሻም የቅንጅት አባላት ብዙ መከራና እንግልት ከደረሰባቸው በኋላ  ለግንቦቱ 7 1997 ዓ.ም ምርጫ ሁከትና  እልቂት ጥፋተኛ ነን ብለው ይቅርታ ጠይቀው ከቃሊቲ መውጣታቸው የማይረሳ የትላንት ትዝታ ነው። በዚህ ጊዜ ለተነሱለትና  ለአመኑለት ዓላማ እስከ መጨረሻዋ ሰዓት ለምን አልቆሙም ያሉ ወገኖች ነበሩ።  በሌላ በኩል ፍርሃት ተሰምቷቸው ድፍረት እንኳን ቢያንሳቸው ያገኙትን  ወንበር  በመያዝ  አዲስ አበባን እያስተዳደሩ  ለለውጥ ተስፋ መሆን ነበረባቸው ያሉም ነበሩ።

 

ከዚህ ላይ አንድ እውነታ አለ። ለውጥ እንዲመጣ ቀስቃሽ ያስፈልጋል፤ የድርጅት መሪዎች ደግሞ ትግሉ ስኬት እንዲያመጣ የግድ የማያቋርጥ የሕዝብ ድጋፍ ያስፈልጋቸዋል። ዴሞክራሲ ተጠማሁ ያለ ሕዝብ መሪዎቹ ሲታሰሩ እጁን አጣጥፎ  መቀመጥ የለበትም። ሕዝቡ የተሰረቀበትን  ድምጽ  ለማስመለስ ትግሉን ማቆም ያለበት አይመስለኝም። ስለዚህ ችግሩን የመሪዎች ብቻ ማድረግ ተገቢ አይመስለኝም።

 

ከዚህ በፊት እንዳልኩት ለውጥ ሊመጣ የሚችለው አገር ውስጥ በሚደረገው ሰላማዊ ሕዝባዊ  የተቃውሞ ትግል  በማድረግ  ነው። የአገር ቤት ተቃዋሚዎች ጥንካሬያቸው አስተማማኝ ባይሆንም በተቃውሞ ሥም እየተንቀሳቀሱ  ነው። እንደሚመስለኝ ከሆነ የፓርቲዎች ችግር አንደኛ የመንግሥት ሰርጐ ገቦች በሚያደርጉት የውስጥ አሻጥር  የድርጅቶች የውስጥ ጥንካሬ  ደህና አይደለም።  እንዲሁም  የውስጥ  ሽኩቻ  አለባቸው። የተለያዩ ፓርቲዎች ዓላማቸው በአገራቸው ዴሞክራሲ እንዲሰፍን፤ ሥልጣን የሕዝብ እንዲሆን የሁላቸውም  ፍላጐት  ይመስለኛል።

 

ነገር ግን አንድነት፤ ውህደት የምትለው ቃል ለምን  እንደምታስፈራቸው  በውል ይህ ነው ማለት ባይቻልም አንዳንዶች የፓርቲ መሪነትን ሥልጣን ማጣት ስለማይፈልጉ ይመስለኛል። ድርጅቶች እንደ ቁጥራቸው ብዛት ፕሮግራማቸውም የተለያየ ነው።  ስለሆነም የአመለካከት ልዩነት ሊኖራቸው ይችላል። ነገር ግን  ለአገርና ለሕዝብ ሲባል መሰረታዊ ሥር-ነቀል ለውጥ ለማምጣት ለምን በጋራ ወይም በያሉበት ተከባብረው ጠንክረው መቆም አቃታቸው የሚለው አሳሳቢ ነው። ስለዚህ የድርጅቶችን አደረጃጀትና  ጥንካሬ ሲቃኝ እጅግ  ውስብስብ  ነው።

 

ተደጋግሞ እንደታየው ድርጅቶች በሥልጣን ይገባኛል በየመድረኩ እስጥ አገባ ሲሉ ይደመጣሉ።  የሚያስገርመውና  የውስጥ ችግሮቻቸውን በሰለጠነ  ሁኔታ ሳይፈቱ፤  ሕዝብ ሳያደራጁና በቂ አባላት ሳይኖራቸው  በብዙ ችግር የተወሳሰበቸውን አገርና  ሕዝብ መምራት  እንችላለን  እያሉ ሲናገሩ  መደመጣቸው ነው። ምኞታቸው ባልከፋ እስየው ያስብላቸዋል። ግን መጀመሪያ አገርና ሕዝብ መምራት እንችላለን ከማለታቸው በፊት ዴሞክራሲን መልመድ ግድ ይላቸዋል። ሌላው የድርጅቶች ድክመት ወይም ችግር ስለኅብረት ትግል በየጊዜው ያወራሉ። ነገር ግን ሌሎች ወደ እነሱ ተጠግተው  ኅብረት እንዳይፈጥሩና ሥልጣን  እንዳይጋሩ በብረት መጋረጃ  በማጠራቸው ኅብረት የሚባለው ከይስሙላ ባለፈ  ተግባራዊ ሊሆን አይችልም። ተሞክሮው ተጨምሮበት ማለቴ  ነው። ይህ ሲባል የማንንም ሞራል ለመንካትና ዝቅ ለማድረግ ሳይሆን  ከሚታየው እውነታ በመነሳት ነው።

በየጊዜው  የተለያዩ  ሰላማዊ  ሕዝባዊ  የተቃውሞ ሰልፎች  ይደረጋሉ። ደም ያልፈሰሰበት ለውጥ ማምጣት ከሁሉም በላይ  ይመረጣል። ነገር ግን የሚደረጉ ሰላማዊ ሰልፎች ግራ ማጋባታቸው አልቀረም። የአንድነት ፓርቲ  ስልፍ ሲጠራ ሌሎች ከጐኑ ቆመው ሰልፉን መቀላቀል ሲችሉ በርቀት ይመለከታሉ። አንድነት ፓርቲ ሰልፉን ካጠናቀቀ በኋላ  ወር ጠብቆ  ሌላው ፓርቲ  ወይም ድርጅት ሰላማዊ  ሰልፍ  ይጠራል። የዚህ ዓይነት የተሰበጣጠር ትግል የት ሊያደርስ እንደሚችል ግልጽ ነው። ስለዚህ የተቃዋሚዎችን እየርስ በርስ ፉክክር ማመላከት ብቻ ሳይሆን የእውነትን  መንገድ አለመከተል ቁልጭ አድርጐ  ያሳያል። “ለተቀማጭ  ሰማይ ቅርቡ” ካልተባልኩ የተናጥሉ ሰላማዊ  ሕዝባዊ  ሰልፍ  ውጤት አያመጣም።  ስለዚህ በተቻለ መጠን የፕሮግራም ልዩነት ቢኖርም እንኳን  አንዱ ፓርቲ የሚጠራው  ሰላማዊ  ሕዝባዊ የተቃውሞ  ሰልፍ  ሁሉን  ሊመለከታቸውና ሊተባበሩ ግድ እንደሚላቸው የሚያጠያይቅ አይመስለኝም።

 

እስከ ዛሬ  አንድነት፤ ኅብረት፤ ውኅደት እየተባለ ብዙ ጊዜ ተደጋግሞ ተሞክሮ አልተሳካም። ወደፊትም ቢሆን በዚህ አካሄድ አይሳካም። ሥር ነቀል ለውጥ  እንዲመጣ  ከተፈለገ  እያንዳንዱ ፓርቲ የራሱን ፕሮግራም ተግባራዊ ለማድረግ ድርጅቱ ከሰርጐ ገቦች ነፃ መሆኑን ማረጋገጥ አለበት። ከዛም  ለአንዲት ኢትዮጵያ ለእውነተኛ ዴሞክራሲ ከሕዝቡ ጐን ሆኖ ከታገለ ስኬታማ ሊሆን ይችላል። ይህን ሲያደርግ ግን ሌሎች ድርጅቶችን በጥላቻ ዓይን መመልከት የለበትም።  የእያንዳንዱ ፓርቲ ማንነት የሚለካው  በሚያደርገው እንቅስቃሴ ነው። ሥልጣን ሊይዝ የሚችለው የሕዝቡን አመኔታ ሲያገኝ ነው። ስለዚህ እያንዳንዱ ፓርቲ   በምርጫ ተሳትፎ የሚያገኘው የሕዝብ ድምጽ ይወስነዋል ማለት ነው። ብዙ ድምጽ ያገኘ መንግሥት ሲሆን ትንሽ ድምጽ ያገኙ ፓርቲዎች እንዲሁ የያዙትን ወንበር ይዘው ወደፊት ፕሮግራማቸውን አሻሽለው ሕዝብ እያደራጁ ለቀጣዩ ምርጫ መዘጋጀት ይችላሉ። ስለዚህ ጨቋኙን ሥርዓት ለማስወገድ የግድ ተቃዋሚዎች እርስ በርሳቸው መጐሻሸም የለባቸውም። ነገር ግን ተቃዋሚ ሆነው እርስ በርሳቸው ፍክክርን ከመረጡ ተጠቃሚው መንግሥት መሆኑ አይቀሬ ነው።

 

ከላይ ይህን ካልኩ ዘንድ ዛሬ ማሰብ የሚገባን ካለፈው ስህተት እንዴት እንማር የሚለው  እንጅ  ያለፈ ታሪክ መውገጥ አያስፈልግም። ይህች ዓለም በሥልጣኔ  ወደፊት እየገሰገሰች ነው። ጊዜያችሁን ተጠቀሙብኝ እያለች ነው። በተለይ በዉጩ ዓለም የሚኖሩ የፖለቲካ ድርጅት መሪዎችና ደጋፊዎች በአጠቃላይ ዳያስፖራው  ከሰለጠነው ዓለም ብዙ ነገሮችን መቅሰም ይችላል። ከአገር ቤት አንድ ወዳጀ  እንዲህ ሲል ይመክረናል። “ ያለንበት ዘመን የሥልጣኔና  የእውቀት ዘመን ነው፤ እንደ ጥንቱ እንደ ጀግኖች አባቶቻችና እንደ አሁኖቹ ገዥዎቻችን  አገርን  በስሜትና በግምት  መምራትና ማሰልጠን  አይቻልም። በአገራችን  ውስጥ ለውጥ እንዲመጣ ከተፈለገ ጥርት ያለና ግልጽ አገራዊ ራዕይ ያላቸውና  የተለያየ አስተሳሰብ የሚያራምዱ ጠንካራ የፖለቲካ ፓርቲዎች መፈጠር አለባቸው። ወይም አሁን ያሉት በሀገራችን እናሰፍናለን የሚሉትን የሕገ የበላይነትና  ዴሞክራሲያዊ  አስራር  ቢያንስ  በራሳቸው  መካከል  በመለማመድ  መጠናከር  አለባቸው።

 

ሁሉም ወይም  አብዛኛው አገር  ወዳድ  ወገን ሁሉ አሁን የሚታየው  ግዴለሽነና  ራስ  ወዳድነት  ተወግዶ  በሀገሩ ጉዳይ ያገባኛል የሚል አስተሳሰብ  እንዲኖረው  በማድረግ በኩል የፓርቲዎች  ዋነኛ  የቤት ሥራ ሊሆን ይገባል። ጠቅለል ባለ መልኩ የጠንካራ ድርጅቶች ጥያቄ ምላሽ ከአገኘና ችግሮቻችን ላይ በጥሞና መነጋገር፤ መግባባትና  መተባበር  ከተቻለ  የምንፈልገውን ሁሉ  ለውጥ ማምጣት  እንችላለን።”

 

ቀደም ሲል እንዳልኩት ተበላሸም አልተበላሸ  የ2007 ዓ.ም  አገራዊ ምርጫ መካሄዱ አይቀሬ  ነው። በመሆኑም  አገር ቤትና ውጭ  የሚገኙ  ፓርቲዎች ለመጭው ምርጫ ዝግጅት እያደረጉ  ስለመሆኑ መረጃ የለኝም። ቢሆንም  እየተዘጋጁ  ይሆናል  የሚል ግምት መስጠት ይቻላል። ምርጫው ሁሉን የሚያሳትፍ ቢሆንም የአገራችን የፖለቲካ ሁኔታ ውስብስብ በመሆኑ ለፓርቲዎችም ሆነ ለመራጩ ከፍተኛ ፈተና ሊሆንበት እንደሚችል  እገምታለሁ።  መንግሥት  የፓርቲዎችን  መኖር  ስለማይፈልግ ሚዲያ እንዳይጠቀሙ መንገዱን ሁሉ  ዘግቶባቸዋል። ጋዜጦችም ቢሆኑ  መንግሥትን  የሚያወድሱ  ካልሆኑ  የተቃዋሚዎችን ሃሳብ የሚያንጸባርቁ ጋዜጦች ታግደዋል። ከዚህ በተጨማሪ ድርጅቶች የበጀት እጥረት ሊኖርባቸው እንደሚችል እገምታለሁ። ሕዝቡም ቢሆን ከዚህ ቀደም በምርጫ ተሳትፎ  ተደጋጋሚ ጊዜ ሽንፈት ስለደረሰበት ተስፋ የቆረጠ ይመስላል።

መረጃዎች እንደሚጠቁሙን ከሆነ  መንግሥት የምረጡኝ ቅስቀሳ ጀምሯል። ባንፃሩ በተቃዋሚዎች በኩል የምረጡኝ ዘመቻ በሁሉም ክፍላተ-ሀግራት  መጀመር  አለባቸው። ሕዝቡም ከተቃዋሚዎች ጐን በመሰለፍ የማቲሪያል የገንዘብ ድጋፍ ሊያደርግላቸው  ግድ ይላል። “የተሳለ ካራ” የእግር ኮቴ አቸውን  እየተከተላቸው የሕዝብ ደሮ ድምጽ የሆኑ ጀግና ጋዜጠኞች የሕዝብ  ድጋፍ  ያስፈልጋቸዋል።  ነገር ግን አብዛኛው ሕዝብ እሩቅ ሆኖ ተቃዋሚዎች  ለውጥ ያመጣሉ ብሎ  የሚገምት ከሆነ  ስሌቱ የተዛባ ይሆናል። በ2007 ዓ.ም ለሚካሄደው አገራዊ ምርጫ ገዥው ፓርቲ አሸነፍኩ ለማለት የተለያዩ ዘዴዎች እየተጠቀመ ስለመሆኑ መረጃዎች ይጠቁማሉ።

 

የአዲስ አበባ መስተዳደር ከሕዝቡ ጋር በተለያየ መንገድ ግንኙነት እንዳለው አይታበልም። በየጊዜው ነዋሪውን እየሰበሰበ ስለ መልካም አስተዳደር መስበክ ከጀመረ ሰነባብቷል። የትራንስፖርት ችግር፤ የውሃ፤ የመብራት አገልግሎት ይሟላል፤ ሥራ አስጥነት ይወገዳል፤ ወደፊት ኅብረተሰቡ በኢኮኖሚ በትምህርት በልማት፤ የባቡር አገልግሎት ተጠቃሚ  እንዲሆን ሌት ተቀን እየሰራን ነው ማለቱን በወቅቱ ስብሰባ ላይ ከነበሩ አንድ አዛውንት አረጋግጫለሁ።

ሕዝቡ የትራንስፖርት፤ የውሃ፤ የመብራት ችግር እንዳለበት አይካድም። ከንቲባውና ሽማምታቱ ችግሩን እንቀርፋለ ማለታቸው መቼስ ተስፋ ጥሩ ነውና አባባላቸው አይጠላም። ግን  የገዥውን  ፓርቲ  ባህሪ አተኩረን ስንመለከት ዴሞክራሲያዊ  እንዳልሆነ ነው። ምርጫ ሲቃረብ የኅብረተሰቡን ችግር እቀርፋለሁ፤ ኢኮኖሚ ያድጋል፤ ዴሞክራሲ  በሽበሽብ  ይሆናል  ይላል። ነገር  ግን  ከምርጫ በኋላ የውሃና የመብራት ችግር  አይኖርም፤ የዋጋ ውድነት፤ የህክምና አገልግሎት እጥረት ይወገዳል ግድ የላችሁም “በኢሕአዴግ ይሁንባችሁ”ማለቱ የተለመደ ነው። ይሁን እንጂ ተደጋግሞ እንደታየው ተግባር ላይ ይውላል ብሎ መገመት ጉም መጨበት ይሆናል።

 

ለማጠቃለል ያህል፦ ያለፈው አልፎ  ወደፊት ለዜጐች እኩልነት፤ ለዴሞክራሲ ለኢትዮጵያ አንድነት  እንታገላለን የሚሉ ሁሉም ዜጋ በቋንቋ፤  በዘር፤  በሃይማኖት ልዩነት ሳይወሰኑ ስፋ አድርገው እየተመለከቱ በአንዲት ኢትዮጵያ ላይ ማተኮር  ይጠበቅባቸዋል። ይህ  የተሰበጣጠረ  ውጥንቅጡ  የወጣ  በቡድንና  በአካባቢ መደራጀት የትም ስለማያደርስ መቆም አለበት። የእከሌ ዘር ጨቋኝ፤ የእከሌ ዘር ተጨቋኝ፤ አማራ፤ ትግሬ፤ ኦሮሞ፤ አገው፤ ጉራጌ ወዘተ እያሉ መከፋፈሉ አገራችን  እየጐዳ  ነው። መጭውን  ትውልድ፤ አገርና ታሪክ አልባ እንዳይሆን ከወዲሁ መጠንቀቅ ተገቢ ይመስለኛል።

 

እያንዳንዱ ሊያስብበትና ሊጠነቀቅበት የሚገባ የዘር ፖለቲካን  እያወገዝ  እግረመንገዳችን  በዘርና  በቋንቋ  መደራጀትን  ከመረጥን  እንዴት ሕወሃትን  ዘረኛ ልንለው  ህሊናችን  ሊፈቅድ  ይችላል የሚለው ነው። ምክኒያቱም መጀመሪያ ዘረኛ ከሚባለው ተሽሎ መገኘት አዋቂነት ብቻ ሳይሆን ግዴታ ሊሆን ይገባል።  በዘር መደራጀት ካንሰር ነው። በዘር መደራጀት  ያለፈ ታሪካና  መውጭውን  ትውልድ  ያረክሳል። ስለዚህ አንዳንዶች  ለእለት ፍጆታ ብለው ውጭ ሆነው መደበሪያና  የገንዘብ ማግኛ  ዘዴ ለማድረግ ሲባል ከዚህ በፊት ያልታየ ዘር ቆጠራ የትም አያደርስ።  ስለዚህ ዘርን  ያማከለ  ቅስቀሳ የሚያካሂዱትን በቃችሁ መስመር  አልፋችኋል ብለን  ፌሽካ ነፍተን  ልናስደነግጣቸው ይገባል። ይህች አገር የሁሉም ናት፤ ማንም ተነስቶ በአገርና በሕዝብ ጉዳይ ወሳኝ ሊሆን  አይፈቀድለትም። ድብብቆሹ  በዚህ ከቀጠለ  አደጋው ሊከፋ እንደሚችል መጠርጠር ቢያንስ ነው። የፉክክር ቤት  ሳይዘጋ  ያድራል  እንዲሉ  ቆም ብለን  መዝጊያ  ልናበጅለት  ግድ  ይላል።

 

 

 


”የፈሪ ዱላው አስር”ኢህአዲግ ፈርቷል።ለመሆኑ ኢህአዲግ ያሰራቸው ምንም አይነት ድብቅ አላማ የሌላቸው የዞን ዘጠኝ ጦማርያን እና ጋዜጠኞች እነማን ናቸው?

0
0

zone 9ፍርሃት የማያሰራው ነገር የለም።ኢህአዲግ በከፍተኛ የፍርሃት ማጥ ውስጥ ነው።ሁሉንም ይፈራል።አይዞህ አትፍራ ቢሉትም የሚችል አይመስልም።በሕዝብ ላይ የሰራቸው ሕዝብ የሚያውቃቸው እና የማያውቃቸው ብዙ ድብቅ ስራዎች ስላሉት የመፍራት ደረጃው ከዕለት ወደ ዕለት እየባሰበት እንጂ እየተሻለው አልሄደም። የሚደግፉትም ልያፅናኑት አልቻሉም።ከሚገባው በላይ ፍርሃት ሲያንቀጠቅጠው ሲመለከቱ እነርሱም ይብሱን ፈሩ።ብዙ የስርዓቱ ደጋፊዎች እና በሀብት የደለደሉቱ ሀገር ጥለው እየወጡ መሆኑን መረጃዎች ያሳያሉ።ይህ ደግሞ ሌላው የፍርሃት ገፅታ ነው።

የዞን ዘጠኝ ጦማርያን እና ሌሎች ሰሞኑን የተያዙት ጋዜጠኞች ምንም የተደበቀ አጀንዳ የሌላቸው ግን ህገ መንግስቱ ላይ የሰፈረው ሃሳብን በነፃነት የመግለፅ መብት ይከበር ያሉ በእዚህም መስረት የሕገ መንግስቱን አንቀፅ እየጠቀሱ የሃሳብ የመግለፅ መብታቸውን የተጠቀሙ፣የሚሰሩት በመንግስት መስርያቤቶች የሆነ፣የሚፅፉት አይደለም ምን በልተው ከማን ጋር ውለው እንዳደሩ መንግስት ብቻ ሳይሆን ሕዝብ የሚያውቃቸው ኢትዮጵያውያን ናቸው።ከእዚህ በፊት በሃሳብ የሞገቱትን ሁሉ ”ህገ መንግስቱን እና ስርዓቱን ለመናድ የተንቀሳቀሱ” እያለ ሲያስራቸው የነበረው መንግስት ዛሬ እራሱ ህገ መንግስቱን አክብረው ሕግ እየጠቀሱ የፃፉትን በ20 ዎቹ እድሜዎች ውስጥ የሚገኙ ወጣቶችን ”ሃገርን በውጭ ከሚኖር ድርጅት ጋር ተመሳጥረው ሊያሸብሩ” እያለ ፌዝ አይሉት ቀልድ መሰል ክስ አቅርቦ ማዕከላዊ እስር ቤት አስገባቸው።ምንም አይነት ወንጀል እንደሌለባቸው እራሱ ኢህአዲግ ያውቀዋል።ግፍ መስራት የማይሰለቸው እና በፍርሃት የተዋጠ መሆኑ ግን የእዚህ አይነቱን ተግባር እንዲቀጥልበት አድርጎታል።

”የፈሪ ዱላው አስር” እንዲሉ የኢህአዲግ አባላት ማታ ኢቲቪ ዜና ላይ የግብፅ፣የየመንን በቅርቡ ደግሞ የዩክረንን የህዝብ ንቅናቄ እያዩ በሰላም መተኛት አልቻሉም።ያ ቀፎው እንደተነካ ንብ የሚተመው ሕዝብ አንድ ቀን እኛም ላይ ይነሳል የሚል ስጋት አድሮባቸዋል።ለእዚህም ማስረጃው ኢቲቪ ባለፈው ሰሞን ያሳየው የዩክሬንን አመፅ የተመለከተ ፊልም መጥቀሱ ይበቃል።ፍርሃታቸውን ደግሞ እነ ሚሚ ስብሃቱ ቀዝቃዛ ውሃ ውስጥ ገብቶ እንደሚንዘፈዘፍ ሰው እየተንቀጠቀጡ ሲናገሩ ሕዝብ ታዝቦ ”ወይ ፍርሃት” ብሏል።ግንቦት 20 ስመጣ ጀግና እንደነበሩ ከሃያ ዓመት በፊት የነበሩ አሮጌ ታንኮች ያሳየናል።መለስ ብለው ደግሞ በፈስ ቡክ እና በጡመራ ፈራን ይላሉ።አጀብ ነው።

ኢህአዲግ ፈራሁ ብሎ ያሰራቸው ንፁሃን ጦማርያን እና ጋዜጠኞች እነማን ናቸው? የወጣቶቹን የስራ መስክ ግልፅነት እና ሙያ ተመልክታችሁ ፍረዱ።ለፈሪዎችም እዘኑላቸው።

1/ ጋዜጠኛ ተስፋለም ወልደየስ 
ለተባበሩት መንግሥታት ዜና አገልግሎት ኢሪን ለረጅም ጊዜ የሰራ የእንግሊዝኛው ‘ፎርቹን’ ጋዜጣ አምደኛ እና ዘጋቢ

2/ ጋዜጠኛ አስማማው ኃይለ ጊዮርጊስ
  አዲስ ጉዳይ መፅሄት ከፍተኛ ኤዲተር
3/ ጋዜጠኛ ኤዶም ካሳዬ 
በአካባቢ ጥበቃ የሰለጠነች በአዲስ ዘመን ጋዜጣ እና በቀድሞው ‘እንቢልታ’ ጋዜጣ ዘጋቢ 
4/ በፍቃዱ ኃይሉ 
የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ባለሙያ፣ብሎገር እና ቅድስት ማርያም ዩንቨርስቲ በሙያው የሚሰራ
5/ አቤል ዋበላ 
የኢትዮጵያ አየር መንገድ ሰራተኛ የአየር መንገዱ ‘ግራውንድ ቴክኒሻን’  
6/ ማህሌት ፋንታሁን 
የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ ምሩቅ በጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ሰራተኛ 
7/ አጥናፍ ብርሃኔ 
የ25 ዓመት ወጣት በፌስ ቡክ ሃሳቡን የሚገልፅ በብሎጉ ላይ ሃሳቡን የገለፀ 
8/ ናትናኤል 
የ 26 ዓመት ወጣት የኢኮኖሚ ባለሙያ፣’የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ባለሙያዎች ማህበር’ አባል
9/ ዘላለም ክብረት 
የሕግ ባለሙያ፣ማስተርሱን ከሰራ ገና ሳምንታት የሆነው በአምቦ ዩንቨርስቲ የሕግ ትምህርት መምህር ናቸው።

ምንጭ - ከጦማርያኑ ውስጥ በውጭ ሀገር የሚገኙት እንዳልካቸው እና ሶልያና ለቪኦኤ የአማርኛው አገልግሎት ሚያዝያ 20/2006 ዓም ከሰጡት መግለጫ የተገኘ።

ጉዳያችን 
ሚያዝያ 21/2006 ዓም

ከዛሬ ጀመሮ የዞን ዘጠኝ ኩሩ አባል መሆኔን አረጋግጣለሁ –ግርማ ካሳ

0
0

zone9-e1398747809895

ርዮት አለሙ፣ እስክንድር ነጋ፣ በቀለ ገርባ …….እያልን ስሞችን መዘርዘር እንችላለን። በብዙ ሺሆች የሚቆጠሩ  ዜጎች ሕገ ወጥና ኢፍትሃዊ  በሆነ መንገድ የታሰሩ ወገኖቻችን፣  ከእሥር እንዲፈቱ ስንጠብቅ ፣ ሌሎች እየተጨመሩ ነው። ከቃሊት ዉጭ ሆነው እነ ርዪትን ሲጎበኙ የነበሩ አሁን እነ ርዮት አለሙን እየተቀላቀሉ ነው።

 

ዞን ዘጠኞች ፣ እነ ጋዜጠኛ ተስፋአለም፣ የሚጽፉትን ፣ የሚጦምሩትን እኛም አንብበነዋል። በድብቅና በሚስጠር አልነበረም ሃሳባቸውን ሲያካፍሉን የነበሩት። የኛ አካል ናቸው። እነማን እንደሆኑ እናውቃቸዋለን። የታሰሩት ወንጀል ስለፈጸሙ አይደለም። ሕግን ስለጣሱ አይደለም። ወንጀላቸው አገራቸውን መዉደዳቸው ነው። ወንጀላቸው ለፍትህ መቆማቸው ነው። ወንጀላቸው ዶር መራራ ጉዲና እንዳሉት፣  ከጫካ የወጡ ግን ጫካ ከነርሱ ያልወጣ፣  ከበስተጀርባ ሆነው እነ ኃይለማሪያም ደሳለኝ እያዘዙ የሚፈልጡና የሚቆርጡ፣ ከሕግ በላይ የሁኑና ለሕግ ደንታ የሌላቸው፣  ጥቂቶች እንዲጽፉ የማይፈልጉት ስለጻፉ ነው። «እነዚህን የሳይበር ስፔስ አርበኞች ልክ ብናገባቸው፣  ሌሎችም ፈርተው አርፈው ይቀመጣሉ»  የሚል የተሳሳተና እንጭጭ አስተሳሰብ ስላላቸው ነው።

 

እንግዲህ ጥያቄዉ «የኛ ምላሽ ምንድነ ነው የሚሆነው ? »  የሚለው ነዉ። የአለም አቀፍ ድርጅቶች፣ በግለሰብ ደረጃ በርካታ ኢትዮጵያዊያን የተሰማንን ሐዘንና ንዴት ገልጸናል። ተገቢም ነው።

 

ነገር ግን ከዚያ አልፈን መሄድ መቻል ያለብን ይመስለኛል። አገዛዙ ዋና ግቡ እኛን ተስፋ ማስቆረጥ ነው።  ገዛ ተጋሩ በሚባል የፓልቶክ ክፍል አንዲት የአገዛዙ ካድሬ ትሁን ደጋፊ፣  አገዛዙ ላይ ችግር ያለንን  ሰዎች  »ፓፕ ኮርኖች» (ፈንድሻውች) ነበር ያለችን። ለጊዜ ቡፍ ብለን ጸጥ የምንል !!!!!!

 

እንግዲህ ምርጫዉ የኛ ነው። እኛ ሚሊዮኖች ነን። እነርሱ ጥቂቶች ናቸው። እኛ ፍቅርን ፣ ሰላምን፣ እኩልነትን አንድነት እንፈልጋለን። እነርሱ ዘረኝነትን፣ ጭካኔን፣ ግፍን፣ መከፋፈልን ይሰብካሉ። እኛ አገራችን በፍቅር እንገባ እንላለን። እነርሱ ግን «እኛ ስልጣን ላይ እንቅይ እንጂ አገር ብትፈልግ ትፈራርስ» ይላሉ። እኛ የዘር፣ የሃይማኖት የጾታ፣ የእድሜ ልዩነት ሳይኖር እያንዳንዱን ዜጋ፣ አዎ ከጠ/ሚኒስተሩ ጀመሮ እስከ ሊስትሮዉ ፣ በስብእናዉና በኢትዮጵያዊነቱ የከበረ ነው እንላለን። እነርሱን ግን« ሁሉንም  አዋቂዎች፣ ፖሊሱም ፣አቃቢ ሕጉም፣ ዳኛዉም፣ ሕግ አውጭዉም፣ ሕግ አስፈጻሚዉም፣ ኢኮኖሚስቱም፣ ኢንጂነሩም እኛ ብቻ ነን። ሌላዉ ከጫማችን በታች ተረግጦ መቀመጥ ነው ያለበት» ይላሉ።

 

እንግዲህ ምርጫው የኛ ነው። እንደ እንስሳ አንገታችን ላይ ማነቆ ታስሮ፣  ጥቂቶች እየጎተቱን እና እንደፈለገ እየተጫወቱበን መኖር፣ ወይም ነጻነታችንን ማወጅ። ዝም ብለን ለጊዜው ብቻ የምንጮህ ፓፕኮርኖች መሆን ወይም አለትን የሚሰባብር ዳይናሚት መሆን። እነርሱ እንደሚፈልጉትና እንደሚመኙት፣ ዝምታን መርጠን፣ አፋችን ዘግተን መቀመጥ፣ ወይም ዳግማዊ ዞን ዘጠኖች በመሆን  የዞን ዘጠኝ  አባላት ቁጥርን ከስድስት፣  ወደ 6 ፣ ስድሳ ሚሊዮን ማሳደግ።  የናንተን አላውቅም እኔ ግን፣ ከዛሬ ጀመሮ የዞን ዘጠኝ ኩሩ አባል መሆኔን አረጋግጣለሁ።

 

መርዛማ እባብ ከመንደፍ ዉጭ፣  ሌላ ነገር አያውቅም። እነርሱም ማሰር እንጂ መፍታት አያውቁም። ዜጎችን ማሸበር እንጂ ማረጋጋት አያውቁም። ኢትዮጵያዉያንን ማዋረድ እንጂ ማክበር አያውቁም። ይህ ለሃያ አመታት የዘለቀ ግፍ አንድ ቦታ ላይ መቆም አለበት። አሁን መቆም አለበት። ሊያስቆሙት የሚችሉት ደግሞ እነ ጆን ኬሪ አይደሉም። እኛ ብቻ ነን።

 

ሚያዚያ 26 (ሜይ 3 ቀን) በአንድነት ፓርቲ የተዘጋጀ የእሪታ ቀን ሰላማዊ ሰልፍ በአዲስ አበባ ይደረጋል። ከብዙ ግፊትና ትግል በኋላ አስተዳደሩ ለሰልፉ እውቅና ሰጧል። ሰልፉ ሰላማዊና ሕጋዊ ሰልፍ ነው። የምንፈራበትም፣  የምንሸሽበት ምንም ምክንያት የለም። ሰልፍ የምንወጣዉ ለፖለቲከኞች ወይንም ለአንድ ፓርቲ ፣ ወይንም ለሌሎች አይደለም። ሰልፍ የምንወጣው ለራሳችን ስንል ነው። «በአዲስ አበባ እድገት አለ። ዴሞክራሲ አለ። ስርዓቱ መቀጠል አለበት። ኢሕአዴ ጥሩ እያደረገ ነው። የታሰሩትም መታሰራቸው ተገቢ ነው» የሚሉ እነ ሚሚ ስብሀቱ ሰልፍ ባይወጡ ብዙ አያስገርምም። ግን በልባችን ለውጥ እየፈለግን፣ መሰረታዊ የመብትና የኢኮኖሚ ጥያቄዎች እያሉን፣ ዝምታን ከመረጥን ግን፣ ይሄን የሚያዚያ 26ቱን ሰልፍ እንደ አንድ መድረክ ተጠቅመን ድምጻችንን ማሰማት ካቃተን ግን፣  ታዲያ እንዴት እንዘልቀዋለን ?

 

እንግዲህ  ከሚሊዮኖች አንዱ እንሁ እላለሁ። እንዉጣ። ድምጻችንን እናሰማ። መብታችንን እናስከበር። የሕዝብ ጉልበትና አቅም ምን ማለት እንደሆነ እናሳይ። ለታሰሩ አጋርነታችንን እንግለጽ። ስድስት ዞን ዘጠኖች ቢታሰሩ ሚሊዮኖች እንደተወለዱ  እናስመስክር።

 

እመኑኝ የሕዝብን ጉልበት ሊቋቋም የሚችል ማንም ኃይል የለም !!!!!!

በሰፊው የኦሮሞ ህዝብ እና ልጆች ላይ እየተፈፀመ ያለውን ግፍ በአጽንኦት እናወግዛለን!!!

0
0

ከአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ የተሰጠ መግለጫ

አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ በኢትዮጵያ የመሬት ስሪት ላይ ግልፅ አቋም እና ፖሊሲ ያለው ፓርቲ መሆኑ ከማንም የተሰወረ አይደለም፡፡ በዚህም መሰረት መሬት በሦስት መሰረታዊ አውድ ላይ እንዲመሰረት ይህም ማለት በወል፣ በመንግስትና በግል ይዞታነት እንዲከበር አቋም ይዞ ይታገላል፡፡ ነገር ግን ከወልና ከመንግስት ውክልና ውጪ ያሉት ይዞታዎች በግል ይዞታነት እንዲከበሩ አቋም ይዞ ይታገላል፡፡ ኢህአዴግ የገጠሩ መሬት የግል ከሆነ አርሶ አደሩ መሬቱን እየሸጠ ወደ ከተማ ይፈልሳል ብሎ ያምናል፡፡ ከምንም የተነሳ ስጋት ነው ባይባልም አንኳ ኢትዮጵያውያን ከመሬት ጋር ያለንን ስነልቡናዊ፣ ማህበራዊና ሁለንተናዊ መስተጋብርን ያላገናዘበና የተጋነነ ስጋት ነው፡፡ ኢትዮጵያውያን ከመሬት ጋር የተለየ ቁርኚት እንዳላቸሰው ለማወቅ ሞታቸውን ሲያስቡ እንኳ “የሀገሬ አፈር ይብላኝ” ሲሉ መመኘታቸው በቂ ማስረጃ ነው፡፡ ኢህአዴጎቹም በቀድሞ ስርዓት ሲተገበር የታገሉትን የመጨቆኛ መሳሪያ ለራሳቸው ሲሆን ተጠቀሙበት፡፡ የሆኖ ሆኖ ይህ የኢህአዴግ ስጋት እውነት ነው እንኳ ቢባል ኢህአዴግ የከተማውን መሬትስ የግል ይዞታ ያላረገው ከተሜው ወዴት እንዳይሰደድ ነው?

ዋናው የገዥው ፓርቲ ፍላጎት መሬትን በጁ በማድረግ የዜጎችን ነፃነት በዚያኑ ያክል ለመሸበብ ነው፡፡  አርሶ አደሩም ሆነ የከተማው ህዝብ መሬት የኔ ነው ብሎ ካመነ ለኢህአዴግ ጫና ስለማያጎበድድ መያዣ ለማድረግ ነው፡፡ የህዝቡ የመሬት ባለቤትነት ቢረጋገጥ በመንግስትና ለኢንቨስትመንት በሚፈለጉ መሬቶች ላይ የመደራደር አቅሙ እጅግ ከፍ ይላል፡፡ መሬቱን በመልቀቁ በሚሰጠው ካሳ (ዋጋም) በቂ የኑሮ ዘዬ ሽግግር የሚያገርግበት አጋጣሚ ይፈጥራል፡፡ ይህ ሊሆን አልቻለም፡፡ በ02/ 08/ 06 ዓ.ም ቡራዩ አካባቢ በተደረገ የመሬት የሊዝ ጨረታ ለተነሺው አርሶ አደር በካሬ 10 ብር የታሰበለት መሬት በጨረታ በካሬ 17 ሺህ ብር መሸጡን ፓርቲያችን ያሰባሰበው ማስረጃ ያሳያል፡፡ በ10 ብር የታሰበለት አርሶ አደር የሚሰደደው በዚህ መልኩ መንግስት ሲቀማው እንጂ የመሬቱ ባለቤት ሆኖና ተደራድሮ በሚሸጥበት ወቅት አልነበረም፡፡

መሬት የምርጫ ድምፅ መያዣ፣ ለኢህአዴግ ገንዘብ ማሰባሰቢያ እና የድጋፍ ምንጭ ሆኗል፡፡ በቅርቡ በጉጂ ዞን ኦዶ ጉዶ አካባቢ ለ2007 ዓ.ም ምርጫ ሞዴል የተባሉ አርሶ አደሮች በቁጥር ከፍ እንዲሉ እንደሹመት ተሰጥቷቸው ሲያበቃ 500 ብር እንዲያዋጡ የመሬት ይዞታቸው ለማስፈራሪያነት መዋሉ እንደማሳያ ሊወሰድ ይችላል፡፡

በሌላ በኩል ምንም አይነት ህዝባዊ ውይይት ሳይደረግበት ከሰማይ ዱብ ያለው የአዲስ አበባ እና ኦሮሚያ ልዩ ዞን የተቀናጀ የልማት መሪ ፕላን ያስቆጣቸው የኦሮሞ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ሰልፍ በማድረጋቸው የደረሰባቸውን ህገ ወጥ ድብደባና እስራት አንድነት በእጅጉ ይቃወማል፡፡ ለእውነተኛ ልማት ነው እንኳ ተብሎ ቢታሰብ ኢህአዴግ ካለበት የተአማኒነት ችግር የተነሳ ተማሪዎቹ ለተቃውሞ አደባባይ ቢወጡ ተፈጥሯዊ እና ህገ መንግስታዊ መብታቸው ሊከበር በተገባ ነበር፡፡ ነገር ግን ሁሉን ነገር ካልጋትኳችሁ የሚለውና ለዴሞክራሲያዊ ሽንፈት የማይገዛው ኢህአዴግ በተማሪዎቹ ላይ ያደረሰውን እንቃወማለን፡፡ የታሰሩ ተማሪዎችም በአስቸኳይ እንዲፈቱም እንጠይቃለን፡፡ የኦሮሞ ተማሪዎችን በገፍ ከዩኒቨርሲቲ የትምህር ገበታቸው በማባረር የሚታወቀው የኢህአዴግ መንግስት ከዚህ ተደጋጋሚ ተግባሩ ታቅቦ ልጆቹን በአስቸኳይ ወደ ትምህርት ገበታቸው እንዲመልስ እንጠይቃለን፡፡

በአጠቃላይ መሬት የዜጎች መያዣ መሆኑ እንዲቀር እንታገላለን፡፡ ዜጎች በመሬታቸው የመደራደር እውነተኛ መብት ሊኖራቸው ይገባል፡፡ ተቃውሞ የሚያነሱ ዜጎችም ድምፅ እንዲሰማ እናሳስባለን፡፡

                                                             አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ

                                                                 ሚያዚያ 22 ቀን 2006 ዓ.ም

                                                                           አዲስ አበባ  

 

UDJ Head

 

ሰበር ዜና- የቀድሞው የአረና ፓርቲ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ አስራት አብርሃምን ጨምሮ ታዋቂ ፖለቲከኞችና ምሁራን አንድነት ፓርቲን ተቀላቀሉ

0
0

ፍኖተ ነፃነት ጋዜጣ

sscgbweui

አቶ አስራት አብርሃም

የቀድሞው የአረና ፓርቲ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ አስራት አብርሃምን ጨምሮ ታዋቂ ፖለቲከኞችና ምሁራን አንድነት ፓርቲን መቀላቀላቸውን አንድ አንድነት ፓርቲ ከፍተኛ አመራር ለፍኖተ ነፃነት ገለፁ፡፡ ከፍተኛ አመራሩ ለፍኖተ ነፃነት እንደገለፁት ታዋቂው ወጣት ፖለቲከኛና ደራሲ አቶ አስራት አብርሃ እና ሌሎች በርካታ ወጣት ምሁራን አንድነት ፓርቲን መቀላቀላቸው ፓርቲው በሀገር አቀፍ ደረጃ በሁሉም የህብረተሰብ ክፍል እያገኘ ያለውን ተቀባይነት የሚያሳይ ነው ብለዋል፡፡ አቶ አስራት አብርሃም በቅርቡ በአንድነት ፓርቲን መቀላቀላቸውን በልዩ መርሀግብር ይፋ እንደሚያደርጉ ይጠበቃል፡፡ በሂደት አንድነትን እየተቀላቀሉ ያሉ የሌሎች ታዋቂ ፖለቲከኞችና ምሁራን ስም ይፋ እንደሚደረግም ከፍተኛ አመራሩ ለፍኖተ ነፃነት ተናግረዋል፡፡ አቶ አስራት አብርሃም “ከሀገር በስተጀርባ”፣ “መለስና ግብፅ” ፣ “ፍኖተ ቃዬል” የሚሉና ሌሎች መጽሓፍትን የጻፉ መሆናቸው ይታወቃል፡፡

 

አንድነት ፓርቲ እሁድሚያዝያ 26 ቀን 2006ዓ.ም “የእሪታ ቀን በሚል” መሪ ቃል ለሚያደርገው ሰላማዊ ሰልፍ ዛሬም የተጠናከረ ቅስቀሳ እየተደረገ ነው፡፡

0
0

በትላንትናው ዕለት በአዲስ አበባ በተያዩ አካባቢዎች የተረገው ቅስቀሳ በፖሊስ ለማስተጓጎልና ለማገት ቢሞከርም በተሳካ መልኩ ተጠናቋል

5

6

3

4

2

1

Viewing all 15006 articles
Browse latest View live