Quantcast
Channel: Ethiopian News | ዘ-ሐበሻ | Latest News Provider | News For All
Viewing all 15006 articles
Browse latest View live

ፖሊሱ ሚኒባሷን በጥይት መታት፤ አንዲት እህት ወዲያው ሞተች ሁለቱ ቆሰሉ

$
0
0

የህዝብን ደህንነት እንዲጠብቁ የሰለጠኑ ፖሊሶች የንፁሀንን ህይወት በማጥፋት ስራ ላይ ተጠምደዋል

news
ትላንትና ማታ ከእምድብር ወደ አዲስ አበባ ይጓዝ የነበረ ሚኒባስ በአካባቢው የጥበቃ ተረኛ በነበረ ፖሊስ በጥይት ከተመታ በኋላ በውስጡ ከነበሩ ተሳፋሪዎች መሀከል የአንድ ከአረብ ሀገር ተመላሽ እህታችን ህይወት ወዲያው ሲያልፍ ሁለት ሰዎች ላይ ደግሞ የአካል ጉዳት ተከስቷል ይላል ለዘ-ሐበሻ የደረሰው መረጃ።

እንደደረሰው መረጃ ከሆነ ፖሊሱ ይህን እርምጃ የወሰደው ሚኒባሱ ኮንትሮባንድ የጫነ መኪና መስሎት እንደሆነ በአካባቢ የነበሩ የአይን እማዬች ቢገልጹም የጥበቃ ፖሊሱ ይህን እርምጃ ከመውሰዱ በፊት ወደ ላይ ተኩሶ መኪናውን ለማስቆም ወይም ለማስጠንቀቅ ያደረገው ጥረት አለመኖሩን አክለው ይገልፃሉ።

አደጋው የደረሰው በጉራጌ ዞን ቸሀ ወረዳ ልዩ ስሙ ጋሶሬ እየተባለ በሚጠራው መንደር ሲሆን በቅርብ ጊዜ ይህ አካባቢ ከወልቂጤ ከተማ ተካሏል) የእምድብር ከተማ ነዋሪ የሆነችው ሟች ኮከቤ አለማየሁ ባለ ትዳር እና የሁለት ልጆች እናት ስትሆን በቅርብ ጊዜ ከአረብ ሀገር ተመልሳ ኑሮዋን ለማቸነፍ አነስተኛ ሱቅ ለመክፈት ለሱቅ እሚሆን እቃ ለማምጣት ወደ አዲስ አበባ እየተጓዘች በነበረበት ጊዜ ነው የለፋችለት ትዳሯን እና መስዋዕት የከፈለችላቸውን ልጆቿን ለሚያሳጣት ጥይት በፖሊሱ የተላከባት። አስክሬኑ ለምርመራ ወደ አዲስ አበባ ምኒሊክ ሆስፒታል ተወስዷል።

ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በመንግስት በታጠቁ ፖሊሶች ህይወታቸው እየተነጠቁ ያሉ ምስኪን ዜጎች ቁጥር በሀገራችን እየጨመረ ይገኛል።

ለሟች ቤተሰቦች ሀዘኑ መራራ ቢሆንም መጽናናትን ለቆሰሉ ቁስላቹ የውሻ ቁስል ይሁንላቹ የሚሉት የዚህ ዘገባ አጠናቃሪዎች “የንፁሀንን ደም ለማጥፋት የሰለጠኑ የሚመስሉትን ፖሊሶችን እያሰለጠኑ ለሚያወጡ ማሰልጠኛዎች እባካችሁ ምልመላና የስልጠና አሰጣጣችሁን በመቀየር ፖሊስ የንፁሀን ጠባቂ እንጂ ስጋት መሆናቸውን አስቁሙልን” ሲሉ ጥሪያቸውን ያቀርባሉ”"


የኑሮ ውድነት ሽክም የጫነብን ማን ይሆን? –(ግርማ ሠይፉ ማሩ)

$
0
0
Girma-Seifu

ግርማ ሠይፉ ማሩ

በሀገራችን የኑሮ ውድነት ከእለት እለት እየከፋ የድሃውን ህዝብ ጉስቁልና እያበዛ እንደሆነ ነጋሪ የሚያስፈልግ አይመስለኝም፡፡ በቤተ መንግሰትና አካባቢ የሚኖሩት ይህ ጉዳይ አይመለከታቸውም፡፡ ለዚህ የኑሮ ውድነት አንዱ እና ዋነኛው ምክንያት የዋጋ ንረት መሆኑን ብዙዎች ይረዳሉ የሚል እምነት አለኝ፡፡ ዛሬ ለፅሁፌ ዋና ማጠንጠኛም የማደርገው የዋጋ ንረት ምንስዔው ምን እንደሆነ በተለይ የመንግሰት ሚና ከዚህ አንፃር ምን እንደሆነ ማስረዳት ነው፡፡

በእኔ አረዳድ በአቅርቦት እጥረት ምክንያት የሚከሰት የዋጋ ንረት አቅርቦቱ ሲሻሻል እንደሚቀንስ በሀገራችን እንደ ሲሚንቶ ያለ ጉልዕ ማስረጃ ማቅረብ አይቻልም፡፡ ከወጣበት ጣራ ወርዶ ትክክለኛም ባይሆን ጥሩ የሚባል ደረጃ ደርሶዋል፡፡ ጊዜው መቼ እንደሆነ ባላስታውሰውም በደርግ መንግሰት ማስታወቂያ ሚኒስትር የሚታተም አንድ መፅሄት “ወደ ላይ ተወርውራ የቀረች ኳስ” ብሎ በሀገራችን ዋጋ ከናረ የማይመለስ ነገር እንደሆነ መጣጥፍ ማቅረቡ ትዝ ይለኛል፡፡ እንደምሳሌ የተጠቀመው ግን አንድ ብር የነበረ ውስኪ ሦሰት ብር ገባ የጠርሙስ ውስኪ ዋጋ ቢቀንስም የመለኪያው አልቀንስ አለ የሚል ነበር፡፡ ይህ ግን የኛ ችግር አይመስለኝም፡፡ የእኛ ችግር ስኳር ቢቀንስ፤ ዱቄት ቢቀንስ፤ ወዘተ የሻይና
የኬክ ብሎም የዳቦና ማኪያቶ ዋጋ ይቀንሳል የሚል ተሰፋ የለንም፡፡ ተስፋችን ለምን ጠፋ? ማን አጠፋው? የዚህ ፅሁፍ ማጠንጠኛ ይሆናል፡፡

 

ገዢው ፓርቲ ኢህአዴግ ወደ መቃብር ካልወረደ ወይም አሁን ያሉተ ሰዎች መቃብር ከመውረዳቸው በፊት የዚህችን ሀገር የመሬት ስሪት የሚለውጥ ነገር ለህዝብ ይዘው በመቅረብ ይህን ጉዳይ ከህገ መንግሰት ድንጋጌነት ማውጣት የሚችሉበትን ዕድል ካልተጠቀሙና ተሰፋ ካልሰጡን ተሰፋችንን ያጠፋው ኢህአዴግ መሆኑ ግልፅ ይሆናል፡፡ አሁን ባለው ሁኔታ ገዢው ፓርቲም እንደሚያምነው አብዛኛው ሌባ የተሰባሰበው በመሬት ዙሪያ ነው፡፡ መሬት የመንግሰት ነው፡፡ በፍፁም የህዝብ አይደለም፡፡ በፓርቲ ተመርጠው በመንግሰት የተሾሙት ሌቦች እንደፈለጉ የሚያዙበት የሀብታቸው ምንጭ ነው፡፡ ይህ እንዴት ዋጋ ያንራል ማለት ተገቢ ነው፡፡ ዋጋ ማናር ብቻ አይደለም ህይወትም ያስከፍላል፡፡ አለማየሁ አቶምሳን ልብ ይሏል!!

 

መንግሰት ዜጎችን እያፈናቀለ በሊዝ የሚቸበችበው መሬት አሁን ባለው ሁኔታ እስከ ሰላሳ ሺ ብር በካሬ ሜትር እየተከፈለበት ነው፡፡ በአዲስ አበባችን፡፡ ይህን በሰላሣ ሺ ብር በካሬ ሜትር የሚገዙ ሰዎች የገንዘብ ምንጫቸው ምንድነው? ብለን መጠየቅ ይኖርብናል፡፡ በህጋዊ መንገድ ያገኘውን ገንዘብ በካሬ ለባዶ መሬት (ወርቅ ውስጡ የሌለ ማለት ነው) ይህን ያህል ገንዘብ ከከፈለ፤ ይህን ገንዘብ ለማስመለስ ግልፅ የሆነው ህጋዊ መስመር መሬቱ ላይ ለሚገነባው ቤት ከፍተኛ ዋጋ መጠየቅ ነው፡፡ ይህ ቤት በሽያጭም ይሁን በኪራይ ውድ ይሆናል ስለዚህ እዚህ ቤት ውስጥ የሚሰጥ አገልግሎት ወይም የሚሸጥ ዕቃም ቢያንስ የቤት ኪራዩን መሸፈን ይኖርበታል፡፡ ስለዚህ ዋጋውን መጨመር የግድ ይላል፡፡ ይህ ትንተና የሚሰራው አዲስ በሚሰሩ በሊዝ ለተገዙ ቤቶች ነው የሚል የዋህ አይጠፋም፡፡ ነገር ግን ቤት አከራዮች አዲሶቹ ዋጋ ሲጨምሩ የድሮዎችም ይህንኑ ተከትለው ነው የኪራይ ዋጋ የሚጨምሩት፡፡ ለምሳሌ በአዲስ አበባ ከተማ ሰርቪስ ቤት በሁለት መቶ ብር ተከራይቶ መኖር የቅርብ ጊዜ ትዝታ ቢሆንም በአሁኑ ሰዓት በምንም ዓይነት አንድ ሰርቪስ ቤት ከሺ አምሰት መቶ በታች ማግኘት አይቻልም፡፡ ከገቢያችን አንፃር ማሰተካከያ ቢሰራለት ይህ ዋጋ አሜሪካን አገር እንኳን እንዲህ ዓይነት ዋጋ የለም፡፡

 

በቅርቡ ከአንደ ጓደኛዬ ጋር የመኖሪያ ቤት ገንብተው የሚሸጡ ሪል ኤስቴቶች አካባቢ ጎራ ብለን ነበር፡፡ እነዘህ ቤት ገንቢዎች ዋጋቸው በፍፁም በሀገር ውስጥ የምንኖር ዜጎችን ያማከለ አይደለም፤ ቤታችንን መንግሰት አይሰራልንም የምንል ዜጎችም ብንኖርም እጃችን ተጠምዝዞ መንግሰትን ደጅ እንድንጠና የሚያደርግ ነው፡፡ ለእነዚህ ቤቶች መወደድ አንዱ ምክንያት የመንግሰት የሊዝ ፖሊስ እንደሆነ መረዳት ብዙ እውቀት የሚጠይቅ አይደለም፡፡ ከዚህ በተጨማሪ እነዚህ ቤት ገንቢዎች ከቤት ገዢዎች የተጨማሪ እሴት ታክስ ሰብሰበው ለመንግሰት ገቢ ያደርጋሉ፡፡ ከቤቱ ዋጋ አስራ አምሰት ከመቶውን የያዘው ለመንግሰት የሚከፈለው ታክስ ነው፡፡ ሌላው የታዘብኩት ነገር ደግሞ ለዋጋ ንረቱ ከሊዝና ታክስ በተጨማሪ ሌላ አቁስል ምክንያት መኖሩ ነው፡፡ ከጋደኛዬ ጋር ቤቱን መግዛት እንዳለብን ከምታግባባን የሽያጭ ሰራተኛ ማዶ ሌላ ሽያጭ ሰራተኛ ሁለት ሴቶችን ከፊት ለፊቷ አሰቀምጣ ቤቱን እንዲገዙ በተመሳሳይ ዝርዝር መረጃ ሰጥታ የማግባባት ሰራዋን ሰታጠናቅቅ፤ በዋጋው ውድነት ብስጭት በማለት የተለያየ ሃሳብ መሰንዘር ይጅምራሉ አንዷ ግን እንደ መፍትሔ ሃሣብ አቅረበች “አንገዛም ማለት አለብን!!” አለች፡፡ ልክ ነበረች ገዢ ሲጠፋ ዋጋ መቀነስ የታወቀ የንግድ ሰርዓት ውስጥ የሚወሰድ እርምጃ ነው፡፡ ትክክለኛ የገበያ ህግ በሚሰራበት ሀገር ማለቴ ነው፡፡ ጓደኛዋ ግን በዚህ መፍትሔ አልተስማማችም እንዲህ አለች “ምን መሰለሽ እዚህ ሀገር ብዙ በህገወጥ መንገድ ገንዘብ የሚያገኙ ሰዎች አሉ፤ እነርሱ ደግሞ በህገወጥ መንገድ ያገኙትን ገንዘብ ህጋዊ ማድረጊያ መንገዳቸው አንዱ ቤት መግዛ ነው” ብላ ተጨማሪውን የዋጋ ንረት ምንጭ ነካችው፡፡

 

ቤት ገንቢዎች ለምን ቤቱን አስወደዱት ብዬ እንደማልከሳቸው ማወቅ አለባቸው ግን በፍፁም ልክ ያልሆነ ነገር በእግረ መንገድ ላስቀምጥ “ይህን ያህል ካሬ ሜትር ቤት በዚይን ያህል ዋጋ” ብለው ማስታወቂያ ሰርተው ለመግዛት የሚሄደው ሰው ግን የሚያገኘው ሰባ ከመቶ ግርማ ሠይፉ ማሩ አይሆንም፡፡ ምን ነው ? ሲባል ለመኪና ማቆሚያ፤ ለመተላለፊያ፤ ለሊፍት፤ ለጋራ አገልግሎት፤ ወዘተ የሚሉ ቦታዎች ተደምረውበታልይባላል፡፡ ይህ ምን ያህል ቤት ፈላጊዎችን እንደሚያሳስት ግን ከሻጮቹም የተሰወረ አይደለም፡፡ ማስታወቂያው ሀቅን መሰረት ያድርግ!! ለቤት ገንቢዎች በእግረ መንገድ ያለኝ ምክር ነው፡፡

 

በዚህች ሀገር የገበያ ህግ እንዳይሰራ እነዚህ ህገወጦች በቀጥታ በጉቦ፣ አገልግሎት በመንፈግ የሚያደርሱብን ጉዳት አልበቃ ብሎዋቸው ሰርቀው ያገኙትን ገንዘብ ህጋዊ ለማድረግ ምስኪን ዜጎች ማረፊያ እንዳይኖረን የሚያደርጉት አስተዋፅኦ እንዲሁም ለዚህም ዋነኛው ተባባሪ በውድ መሬት የሚቸበችበው መንግሰት መሆኑ ታሰቦኝ፤ እንደ አዲሰ እውቅት መብገን ጀመርኩና እናንተም ትበግኑ ዘንድ ነው ይህን ላካፍላችሁ የወደድኩት፡፡ እንግዲ ይህ ገፊ ምክንያት ሆኖን የመሬት ሰሪቱ በዕለት ከዕለት ኑሮዋችን መጥቶ እያሰቃየን ነው ብልን ለለውጥ ካልተነሳን፣ ሌላ ምን በቂ ምክንያት ነው የምንጠብቅው? የሚለው ጥያቄ በእንጥልጥል የሚቆይ ነው፡፡

 

በህጋዊ መንገድ መሬት የሚፈልጉ ሰዎችም ከህገወጦቹ ጋር ነው ግብ ግብ የሚያያዙት፡፡ ለዚህም ዋናው ምክንያት የቁጥ ቁጥ መሬት አቅርቦት ፖሊስ ነው፡፡ መንግስት የመሬት አቅርቦቱን ሆን ብሎ እያሳጠረ፤ ሌቦቹ እንዲመቻቸው ዕድል እንዲፈጠር እያደረገ ነው፡፡ መሬት በመግቢያዬ እንዳልኳችሁ የመንግሰት ነው እንጂ በፍፁም የህዝብ አይደለም፤ ህዝብማ በመንግሰት እጅ በተያዘ መሬት ሰበብ የሻይና ማኪያቶ ዋጋ ላይ ጭምር ጫና የሚፈጥር ሆኖበታል፡፡ የዚህ መሬትን በመንግስት እጅ የማቆየት ፖሊስ ዋናው ገፊ ምክንያት ፖለቲካም መሆኑን መዘንጋት የለብንም፡፡ መሬቱን ይዞ የሊዝ ሂሣብ ሳይከፍል፣ ተጨማሪ እሴት ታክስ ሳይኖርበት፣ ግብዓቶችን ከቀረጥ ነፃ አሰገብቶ ኮንዶሚኒየም በርካሽ እሰራላሁ እያለ ለዚህም በስልጣን መቆየት አለብን እያለ ይገኛል፡፡ ገዢው ፓርቲ፡፡ ዋናው ፖለቲካዊ ግቡ በስልጣ ገዢውን ፓርቲ ማቆየት ነው፡፡ ይህ ገዢ ፓርቲ በስልጣን ላይ ከቆየ ገዢ መደቦች እየሰረቁ ገንዘብ ያገኛሉ፤ በስርቆት ያገኙትን ገንዘብ ደግሞ በውድም ቢሆን መሬት በመግዛት ዘላቂ ጥቅማቸውን የሚያስጠብቅላቸው በኢኮኖሚ ደንዳና የሆነ ሰርዓት ይገነባል ብለው ያምናሉ፡፡ ይህች ፍልሰፍና ግን የብዙሃኑን ተጠቃሚነት በጎዳ መልኩ ስለሆነ እየተሰራ ያላው በምንም መልኩ ሊሳካ የሚችል አይደለም፡፡ በአሸዋ ላይ የተሰራ ቤት ዓይነት ነው፡፡ አውሎ ንፋስ አይጠብቅም ትንሽ ንፋስ ጠራርጎ ያፈርሰዋል፡፡ ልብ መግዛት ያለብን ይመስለኛል፡፡

 

ፅሁፌን ከዘጋው በኋላ ዋጋው በአቅርቦት መሻሻል ይቀንሳል ብለን ተሰፋ ያደረግነው ሰኳርም ቢሆን የዋጋ ጭማሪ ያደረገ መሆኑን በሬዲዮ ሰማው፡፡ ይህ ምንም አያስገርምም፡፡ የሚያስገርመው መግለጫ የሰጡት ኃላፊ ማብራሪያ ነው፡፡ የዋጋ ጭማሪ የሚባል ነገር የለም፡፡ ነገር ግን ለትራንስፖርት ተብሎ ዘጠና አምሰት ሳንቲም በኪሎ ተጨመረ እንጂ፤ የዚህ ምክንያት ደግሞ ቀደም ብሎ ሰኳሩ ከውጭ ስለሚመጣ ከጅቡቲ በቀጥታ ይገባ ስለነበር ነው፡፡ በማለት ቀደም ሲል ስኳር የትራንሰፖርት ወጪ የለበትም የሚል መንፈስ ያለው መግለጫ ሰጡ፡፡ ይህ መግለጫ ህዝቡን እንዴት እንደናቁት ከማሳየት ውጪ አንድም የእውቀትና እውነት መሰረት የለውም፡፡ የዋጋ ጭማሪ አይደለም የትራንሰፖርት ነው!! ምን የሚሉት ፌዝ ነው፡፡ ዋጋ እንዴት ነው የሚተመነው? ፋብሪካው ይህ የመጀመሪያ ምርቱ ነው? እሰከዛሬ ትራንስፖርት ማን ነበር የሚሸፍነው? መግለጫውንም ሁሉንም ትተን አሁንም ቢሆን በተጨመረው ዋጋ ስኳሩ የታለ ነው? ያለው ጭማሪውን ዋጋም ጨምሮ ይገዛል፡፡ የሌለው ድሮ ከሚገዛው መጠን ቀንሶ ይገዛል፡፡ በተለይ የመንግሰት ሰራተኛው በቅርቡ የትራንሰፖርት ዋጋ ተጨመረበት፣ አሁን ደግሞ የስኳር ማጓጓዣ ተጨመረበት፣ ቀጥሎ ስኳርን ተከትሎ ዳቦ ይጨምራል ወዘተ.. ደሞዝ ግን እንዳለች ነው፡፡ መፍትሔው ልጆችን ስኳር ለጤና ጥሩ አይደለም ብሎ ማስተው ነው፡፡ ዳቦ እንዴት ተብሎ ይከለከል ይሆን?

 

ታስታውሱ እንደሆነ የተለያዩ ምክንያቶችን እየደረደረ ዋጋ ይጨምር የነበረው ሙገር ሲምንቶ ፋብሪካ አሁን ዋጋ መቀነሱን ማስታወቂያ ከፍሎ እየነገረን ነው፡፡ ምክንያቱም የመንግሰት ያልሆኑ ተወዳዳሪዎች ስለመጡበት እና እየመጡበት ስለሆነ ነው፡፡ ስኳር ይህን እድል እንዳያገኝ ማዕቀብ ያደረገብን መንግሰት ነው፡፡ ሁሉም ፋብሪካ እኔ እስራለሁ ብሎ፡፡ ቢሰራውም ዋጋ አይቀንስም፡፡ ለምን? የሚታለብ ላም ነው ይለናል፡፡ ስለዚህ ይህን የኑሮ ውድነት የጫነብን እየጫነብንም ያለው፣ በመንግሰት ስም የተቀመጠው የአብዮታዊ ዲሞክራሲ ዘራፊ ቡድን ነው፡፡ ቸር ይግጠመን፡፡

የአቶ ድሪባ ኩማ አስተዳደርና በቅሬታ የምትናጠው አዲስ አበባ

$
0
0

<div>ረፖርተር
መጋቢት 22, 2006 ዓ.ም
በአዲስ ከንቲባና ነባር ካቢኔ ሥራውን የጀመረው የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሰባተኛ ወሩን ይዟል፡፡

አስተዳደሩ የቆየባቸው ሰባት ወራት የሥራ ክንውን የከተማውን ነዋሪዎች ብሶትና ችግር የፈታ ሳይሆን፣ የመልካም አስተዳደር ችግሮች ጐልተው የታዩበት ነበር ማለት ይቻላል፡፡

የአቶ ድሪባ ኩማ አስተዳደርና በቅሬታ የምትናጠው አዲስ አበባከ2001 ዓ.ም. እስከ 2005 ዓ.ም. ለአምስት ዓመታት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደርን በከንቲባነት ሲመሩ ከነበሩት አቶ ኩማ ደመቅሳ የአዲስ አበባ ማዘጋጃ ቤትን ቁልፍ የተረከቡት አቶ ድሪባ ኩማ፣ የከተማውን ነዋሪዎች ሲያንገሸግሻቸው የቆየውን የመልካም አስተዳዳር እጦት ችግር በመጠኑም ቢሆን ይፈቱታል የሚል ግምት ተሰጥቶዋቸው እንደነበር ሪፖርተር ያነጋገራቸው አንዳንድ የከተማው ነዋሪዎች ተናግረዋል፡፡ ነዋሪዎቹ ቅድሚያ ግምት የሰጡት ዝም ብለው ሳይሆን በፌዴራል መንግሥት ጭምር ትኩረት ተሰጥቶ መሠራት ያለባቸው በዋናነት፣ የመልካም አስተዳደር እጦትና የሙስና ጉዳዮች በመሆናቸው ጭምር ነው፡፡ የፌዴራል መንግሥት መቀመጫ የሆነችው አዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎች ለሚጠይቋቸው የመብትም ሆነ ሌሎች ጥያቄዎች ተገቢ የሆነ ምላሽ ማግኘት ባለመቻላቸው፣ የመልካም አስተዳደር እጦትን በማንሳት ጠዋት ማታ ሲያማርሩ መክረማቸው የአደባባይ ሚስጥር መሆኑን አስተያየት ሰጪዎቹ ይገልጻሉ፡፡

የከተማውን ነዋሪዎች ብሶትና የዕለት ከዕለት ምሬት የተሰማቸው በሚመስል ሁኔታ፣ የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊን ተክተው የተመረጡት ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝም ትኩረት ሰጥተው ከሚንቀሳቀሱባቸው የሥራ ዘርፎች መካከል በዋነኛነት የጠቀሷቸው የመልካም አስጸዳደር እጦትንና ሙስናን መዋጋት እንደነበር ነዋሪዎች ያስታውሳሉ፡፡

ለአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አዲስ ከንቲባ መሾሙን ተከትሎ፣ በአስተዳደሩ መዋቅር ላይ ለውጥ ተደርጐ የአገልግሎት አሰጣጥ ለውጥ ያመጣል የሚል ግምትም ነበር፡፡ አስተዳደሩም ለውጥ ለማምጣት ቆርጦ የተነሳ በሚመስል ሁኔታ ለሰው ኃይሉ ግምገማዊ ሥልጠና ሲሰጥ ቆይቷል፡፡ በሥልጠናውም 500 ከፍተኛ አመራሮች፣ 3,000 መካከለኛ አመራሮችና 52 ሺሕ ሠራተኞች ተሳትፈዋል፡፡

<a href=”http://www.zehabesha.com/wp-content/uploads/2014/03/የአቶ-ድሪባ-ኩማ-አስተዳደርና-በቅሬታ-የምትናጠው-አዲስ-አበባ.jpg”><img class=”size-medium wp-image-26797 alignleft” alt=”የአቶ ድሪባ ኩማ አስተዳደርና በቅሬታ የምትናጠው አዲስ አበባ” src=”http://www.zehabesha.com/wp-content/uploads/2014/03/የአቶ-ድሪባ-ኩማ-አስተዳደርና-በቅሬታ-የምትናጠው-አዲስ-አበባ-300×187.jpg” width=”300″ height=”187″ /></a>ነገር ግን መልካም አስተዳዳርን በማስፈንም ሆነ በአገልግሎት አሰጣጥ ላይ የኅብረተሰቡ ቅሬታ የሚፈታ አልሆነም፡፡ በዋናነት የመልካም አስተዳደር እጦት ከሚስተዋልባቸው የሥራ ዘርፎች መካከል መሬትና መሬት ነክ ይዞታዎች፣ የትራንስፖርት አቅርቦት፣ ንፁህ የመጠጥ የውኃ አቅርቦት፣ የመኖሪያ ቤት አቅርቦትና በአስተዳደሩ ሥልጣን ክልል ውስጥ ባይሆንም የኤሌክትሪክ መቆራረጥና የቴሌኮሙዩኒኬሽን ችግሮች በስፋት የሚስተዋሉ ናቸው፡፡

<em><strong>መሬትና መሬት ነክ ይዞታዎች</strong></em>

የሙስና መፈንጫ ናቸው ተብለው ከተፈረጁ አራት ዘርፎች መካከል አንዱና ዋነኛው መሬትና መሬት ነክ ይዞታዎች ዘርፍ ነው፡፡ በተለይ የቀድሞው ከንቲባ አቶ ኩማ ደመቅሳ የአስተዳደሩን ሥልጣን ከተረከቡበት ከ2001 ዓ.ም. ጀምሮ በዘርፉ ማሻሻያ ለማድረግ ብዙ ሥራዎች ተሠርተዋል፡፡

ከተሠሩት ሥራዎች መካከል የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመሬት ዘርፍን መዋቅር መለወጥ፣ የሰው ኃይሉን ማሟላትና ለሥራው ብቁ ማድረግ ነው፡፡ የሕግ ክፍተቶችን ለመሙላት ደግሞ የፌዴራል መንግሥት የከተማ ቦታን በሊዝ ስለመያዝ አዋጅ በኅዳር ወር 2004 ዓ.ም. ወጥቷል፡፡ በዚህ አዋጅ መነሻነት በርካታ ደንቦችና መመርያዎች በአስተዳደሩ ወጥተዋል፡፡

በዚህ መሠረት አስተዳደሩ የመሬት ልማትና ማኔጅመንት ቢሮ ከማቋቋሙም በተጨማሪ፣ በሥሩ የግንባታ ፈቃድ አሰጣጥና ክትትል ባሥልጣን፣ የይዞታ አስተዳደር የሽግግር ጊዜ አገልግሎት ፕሮጀክት ጽሕፈት ቤት፣ የመሬት ልማትና ከተማ ማደስ ኤጀንሲና የመሬት ባንክና ማስተላለፍ ኤጀንሲ መሥሪያ ቤቶች እንዲቋቋሙ ተደርጓል፡፡

እነዚህ መሥሪያ ቤቶች የሚመሩባቸው ሕግጋትና ልዩ ልዩ የሕግ ማዕቀፎች ከመውጣታቸውም በተጨማሪ የሰው ኃይል እንዲሟላላቸው ተደርጓል፡፡

ከአቶ ኩማ ደመቅሳ ሥልጣኑን የተረከቡት አቶ ድሪባ ኩማ የሥልጣን ዘመን፣ የመሬት ዘርፍ በተቀመጠው ዕቅድ መሠረት ቢደራጅም ሙሉ በሙሉ ማለት በሚቻል ሁኔታ በአገልግሎት አሰጣጡ ላይ ነዋሪዎች ቅሬታ ማንሳታቸው አልቀረም፡፡

በመሬት ተቋማት ላይ እየቀረቡ ከሚገኙ ቅሬታዎች መካከል ከዓመታት በፊት የቀረቡ የመሬት ጥያቄዎች ምላሽ አለማግኘታቸው፣ ለአገር ይበጃሉ የተባሉ ፕሮጀክቶች የሚያቀርቡት የማስፋፊያ ቦታ ጥያቄዎች አለመስተናገዳቸው፣ ለዓመታት ታጥረው የተቀመጡ ቦታዎች ላይ ዕርምጃ አለመወሰዱ፣ ለጥቃቅን ጉዳዮች ሳይቀር ውሳኔ የሚሰጥ አመራር መጥፋት የሚሉት ተጠቃሾች ናቸው፡፡ ከዚህ በተጨማሪም የሰነድ አልባ ይዞታዎች ካርታ አሰጣጥ የተጓተተ መሆኑና ለተነሺዎች የሚሰጠው ካሳ ፍትሐዊ አለመሆኑ ከሚነሱ ችግሮች መካከል ይጠቀሳሉ፡፡

አስተዳደሩ እነዚህን ችግሮች በተመለከተ ያለው አቋም በሕግ መሠረት ሊስተናገዱ የማይችሉ ናቸው የሚል ነው፡፡ አለፍ ሲልም ‹‹ችግሩን ተገንዝበናል፣ የኅብረተሰቡን ቅሬታ እንደ ግብዓት ወስደናል…›› የሚል መሆኑን ጥያቄያቸው ያልተመለሰላቸው ነዋሪዎች ይናገራሉ፡፡ የሊዝ ሕጉ በዋነኛነት መሬት የሚቀርበው በጨረታ አግባብ ነው ይልና የከተማው ከንቲባ ግን ፋይዳ ያለው ፕሮጀክት ነው ብለው ካመኑ ለካቢኔ ቀርቦ በልዩ ሁኔታ ሊስተናግድ እንደሚችል ይገልጻል፡፡

ነገር ግን ፋይዳ አላቸው ተብለው በልዩ ሁኔታ ይስተናገዳሉ የሚባሉት ፕሮጀክቶች በግልጽና በዝርዝር ባለመቀመጣቸው፣ የመሬት ቢሮ ሠራተኞች የሚቀርቡላቸውን ጥያቄዎች ለማስተናገድ ዝግጁዎች እንዳይሆኑ አድርጓል ሲሉ የሕግ ባለሙያዎች ይናገራሉ፡፡

በዚህ ምክንያት የከተማው የሊዝ ማስፈጸሚያ መመርያና በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የፀደቀው የሊዝ አዋጅ ብዙም ሥራ ላይ ሳይውሉ እንዲሻሻሉ መመርያ መሰጠቱ እየተነገረ ነው፡፡ ከዚህ በተጨማሪ ባለሀብቶች ቀደም ሲል የቀረቡት የመሬት ጥያቄዎች ሊስተናገዱ ባመቻላቸው ቅሬታቸውን ለጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት እያቀረቡ ይገኛሉ፡፡

የከንቲባው ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ አሰግድ ጌታቸው ለሪፖርተር እንደገለጹት፣ ወደ ጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት የሚያስኬዱ አንዳንድ ነገሮች መኖራቸውን፣ የሊዝ አዋጁና የሊዝ አዋጅ ማስፈጸሚያ የትርጉም ችግር ከመጣ እንደሚሻሻል ጠቅሰው፣ የመሬት አቅርቦትን በተመለከተ ግን አስተዳደሩ ትኩረት አድርጎ የነበረው ለኮንዶሚኒየምና ለ40/60 ቤቶች የሚያስፈልጉ ቦታዎችን ማቅረብ ነው፡፡ ለጨረታ የሚቀርቡ መሬቶችን በማዘጋጀት በኩል የተወሰኑ መጓተቶች እንደነበሩና በሚቀጥሉት ወራት ለጨረታ የሚቀርቡ ቦታዎች ላይ ትኩረት እንደሚደረግ አቶ አሰግድ ተናግረዋል፡፡ አስተዳደሩ በዓመቱ መጀመርያ ላይ 1,200 ሔክታር መሬት ለሊዝ ጨረታ እንደሚያቀርብ ገልጾ ነበር፡፡ ነገር ግን በእስካሁኑ ቆይታ የዚህን ዕቅድ ሩብ እንኳ ለገበያ አለማቅረቡን በርካታ ሰዎች ይናገራሉ፡፡

በመሬት ዘርፍ ችግር የነበሩ ጉዳዮችን የቀድሞ አስተዳደር ቅርፅ አስይዞታል የሚሉ በርካታ የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎችና ባለሀብቶች፣ ከከንቲባ ድሪባ ኩማ በርካታ አገልግሎቶች ቢጠብቁም እንዳልተሳካላቸው እየገለጹ ነው፡፡

<em><strong>ውኃ</strong></em>

አስተዳደሩ በግማሽ ዓመት የሥራ አፈጻጸሙ ጥሩ እየተሠራ መሆኑን የገለጸው አንዱ ንፁህ የመጠጥ ውኃ አቅርቦትን በሚመለከት ነው፡፡ ንፁህ የመጠጥ ውኃ ጥልቅ ጉድጓዶችን በመቆፈርና ግድቦችን በማስፋፋት እንደሚያቀርብ ገልጿል፡፡ አስተዳደሩ ውኃን በሚመለከት በስድስት ወራት ውስጥ የሠራውን ግልጽ ሆኖ በሚታይ ሁኔታ ባያስቀምጥም፣ በጥቅሉ በበጀት ዓመቱ እየሠራቸው ያሉትንና ሊሠራቸው ያቀዳቸውን ተናግሯል፡፡ በበጀት ዓመቱ በአቃቂ 19 ጥልቅ ጉድጓዶችን እየቆፈረ መሆኑንና 80 ሺሕ ሜትር ኩብ ውኃ ማምረቱን በሪፖርቱ ቢገልጽም ወደ ሥርጭት አልገባም፡፡ በለገዳዲ ደግሞ 11 ጥልቅ ጉድጓዶችን መቆፈር መጀመሩንና ሲጠናቀቅ 40 ሺሕ ሜትር ኩብ ውኃ ማምረት እንደሚጀምር ይናገራል፡፡ የድሬ ግድብን በማሻሻልና የለገዳዲ ማጣሪያን በማስፋፋት የውኃን ምርት ወደ 195 ሺሕ ሜትር ኩብ ለማሳደግ እየሠራ መሆኑንም በሪፖርቱ ገልጿል፡፡

በአጠቃላይ አስተዳደሩ የውኃ ምርትን በማሳደግ በኩል ከፍተኛ የሆነ ሥራ እየሠራና የጀመራቸው የጉድጓድ ቁፈራ፣ ግድብ ማስፋፋትና የክረምት ውኃ ጥበቃን በሚመለከት በኩራት እየተናገረ ቢሆንም፣ በከተማው ውስጥ እየታየ ያለው እውነታ ግን የተገላቢጦሽ መሆኑን ሁሉም ነዋሪዎች ይስማሙበታል፡፡

በከተማው በተለይ ባለፉት አራትና አምስት ወራት ውስጥ የውኃ ችግር በከፍተኛ ሁኔታ ምሬት እየፈጠረ ነው፡፡ ቀደም ባሉት ጊዜያት የውኃ እጥረት ያለባቸው የከተማው አካባቢዎች ዳገታማ ቦታዎችና ከማሠራጫ ጣቢያዎች ርቀው የሚገኙ ሲሆን፣ በአሁኑ ጊዜ ግን ከማዕከል አካባቢዎች ጀምሮ የውኃ ችግር ከፍተኛውን ቦታ ይዞ ይገኛል፡፡ የመሠረተ ልማቶች መስፋፋት ለውኃ እጥረት በምክንያትነት ቢጠቀሱም፣ ነዋሪዎች ግን አይስማሙም፡፡ አዲስ አበባ ከተማ እየሰፋች መሆኗን ሁሉም ነዋሪዎች የማይክዱት ሀቅ ነው፡፡ ነገር ግን ከከተማው መስፋፋት ጋር ተያይዞ አስተዳደሩ ትኩረት ሰጥቶ ሊሠራባቸው ከሚገቡ ነገሮች አንዱና ዋነኛው በቂ የውኃ ምርት ማቅረብ ላይ መሆኑን አንድ ስማቸው እንዲገለጽ ያልፈለጉ የከተማው የውኃና ፍሳሽ ባለሥልጣን ባልደረባ ይናገራሉ፡፡ ባለሥልጣኑ በንፁህ የመጠጥ ውኃ አቅርቦትና ፍሳሽ ማስወገጃ ሥራዎች ላይ ትኩረት ሰጥቶ የሚናገረውና ለመንቀሳቀስ የሚሞክረው በበጀት ዓመቱ መጀመሪያ ወራትና በበጀት መዝጊያ ወቅት መሆኑን ሠራተኛው ይናገራሉ፡፡

የበጀት ዓመቱ ሲጀመር በተለይ ውኃ የማይደርስባቸው ቦታዎች ይመረጡና ቅድሚያ ተሰጥቶ እንዲሠሩ በሚል ብዙ ገንዘብ ወጪ እንደሚደረግ የሚናገሩት ሠራተኛው፣ ፕሮጀክቶቹ ከጅምር ቁፋሮ ሳያልፉ በኃላፊዎች የወረቀት ላይና የዓውደ ጥናት ፕሮፓጋንዳ ታጅበው በጀት ዓመቱ እንደሚጠናቀቅ ጠቁመዋል፡፡ በጀት ዓመቱ ሊዘጋ ወር ሲቀረው፣ በተለይ ፍሳሽ ለማስወገድ በሚል የክረምቱን ጭቃ የሚያባብሱ ቁፋሮዎች በየመኖሪያ ሠፈሮች ይቆፈሩና የተረፈው በጀት እንዲጣጣ እንደሚደረግም አክለዋል፡፡ ይኼ አሠራር የተለመደና አሁንም መልኩን ቀይሮ የተለያዩ ሰበቦች እየተደረደሩ፣ ማለትም የመንገድ ሥራ፣ የባቡር ሀዲድ ዝርጋናታና ሌሎችም ምክንያቶች እየቀረቡ የኅብረተሰቡ ንፁህ የመጠጥ ውኃ የማግኘት ችግር ተባብሶ መቀጠሉን አውስተዋል፡፡

የባለሥልጣኑ ባልደረባ እንደገለጹት፣ የአዲስ አበባ ነዋሪዎች ንፁህ የመጠጥ ውኃ እጦት ከቀናት አልፎ ወራትንም እያስቆጠረ መሆኑን እየገለጹ ናቸው፡፡ በወረቀት ላይ በሚቀርብ ሪፖርት ብቻ የከተማውን የንፁህ መጠጥ ውኃ ችግር ለመፍታት የጉድጓድ ቁፋሮና የግድብ ማስፋፋት ሥራ እያከናወነ ባለበት ሁኔታ፣ ችግሩ ከ25 እስከ 30 ዓመታት የሚወገድበትን ፕሮጀክት ዘርግቶ እየሠራ መሆኑን በስድስት ወራት ያቀረበውን የአፈጻጸም ሪፖርት ነዋሪዎች ውድቅ አድርገውታል፡፡

<em><strong>የቤቶች ልማት ፕሮግራም</strong></em>

አስተዳደሩ ትኩረት ሰጥቶ እየተንቀሳቀሰበት መሆኑን ከሚናገርባቸው ተቀዳሚ ተግባራት መካከል የነዋሪዎችን የመኖሪያ ቤት ችግር መቅረፍ ይገኝበታል፡፡ በመሆኑም በከንቲባ ኩማ ዘመን የተጀመሩና ያልተጠናቀቁ 95 ሺሕ የጋራ መኖሪያ ቤቶችን ማጠናቀቅና በበጀት ዓመቱ የ65 ሺሕ ቤቶችን ግንባታ ለማስጀመር መሆኑንም መናገሩ ይታወሳል፡፡ በመሆኑም በ2003 ዓ.ም. የተጀመሩ 17,171 የጋራ መኖሪያ ቤቶች ግንባታን 92 በመቶ ማጠናቀቁን ጠቁሟል፡፡ በ2004 በጀት ዓመት ደግሞ በማስፋፊያና መልሶ ማልማት በ16 የተመረጡ ቦታዎች 44,709 ነባር የጋራ መኖሪያ ቤቶችን ግንባታ እያፋጠነ መሆኑንም በስድስት ወራት የሥራ አፈጻጸሙ ላይ አስታውቋል፡፡ ለሌሎች ዝቅተኛ ገቢ ላላቸው ነዋሪዎች 33,593 ቤቶችን ግንባታ እያፋጠነ መሆኑንና ለ40/60 ቁጠባ ቤቶች ተመዝጋቢዎች በአራት ሳይቶች እየገነባ መሆኑን በሪፖርቱ አካቷል፡፡

የጋራ መኖሪያ ቤቶችን ግንባታ በሚመለከት አስተዳደሩ በቅርቡ የመሠረት ድንጋይ ያስቀመጠበትን የ50 ሺሕ ቤቶች ግንባታ ጨምሮ በጥሩ ሁኔታ እየሠራ መሆኑንና የነዋሪዎችን የመኖሪያ ቤት ችግር ለመፍታት ከፍተኛ ጥረት እያደረገ እንደሆነ፣ በተለያዩ አጋጣሚዎች ከመናገር አላረፈም፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ ነዋሪዎች የመኖሪያ ቤትን በሚመለከት የሚናገሩትና አስተዳደሩ ‹‹እየሠራሁ ነው›› የሚለው ግን የሚጣጣምና የሚገናኝ አይደለም፡፡

የመኖሪያ ቤትን ችግር ለመቅረፍ በሚል የኮንዶሚኒየም ቤቶች ግንባታ ጽንሰ ሐሳብ የተጀመረው በ1996 ዓ.ም. ዶ/ር አርከበ ዕቁባይ የከተማው ከንቲባ በነበሩበት ዘመን መሆኑ ይታወሳል፡፡ በወቅቱ ተጋግሎ በነበረው የምርጫ 97 የምረጡኝ ቅስቀሳ ተከትሎ የመጣው የጋራ ቤቶች ግንባታ ምዝገባ፣ በአብዛኛው የከተማ ነዋሪዎች ብዙም ትኩረት አልተሰጠውም ነበር፡፡ ቢሆንም ግን በወቅቱ ከ453 ሺሕ በላይ ነዋሪዎች መመዝገባቸው ይታወሳል፡፡ ለተከታታይ ዘጠኝ ዓመታት ድጋሚ ምዝገባ ሳይደረግ፣ በ1996 ዓ.ም. ብቻ ለተመዘገቡ ቤት ፈላጊዎች አንድ መቶ ሺሕ ያልሞሉ የጋራ መኖሪያ ቤቶች ከሰባት ጊዜ በላይ በዕጣዎች፣ ከዕጣ በተጨማሪም በልማት ምክንያት ለሚነሱ ነዋሪዎችና በትዕዛዝ ለተሰጣቸው ሰዎች ተከፋፍለዋል፡፡ በ2005 ዓ.ም. መጨረሻ ወራት ላይ በተደረገው ዳግም ምዝገባ ከ800 ሺሕ በላይ ነዋሪዎች ሊመዘገቡ ችለዋል፡፡ አስተዳደሩ ምዝገባውን በአራት የተለያዩ ፕሮግራሞች ከፋፍሎ አካሂዷል፡፡ 10/90፣ 20/80፣ 40/60 እና የመኖሪያ ቤት ኅብረት ሥራ ማኅበራት በሚል፡፡

በመኖሪያ ቤት ችግር የሚሰቃዩ ነዋሪዎች ከሚያገኙት ገቢ ላይ በየወሩ እንዲቆጥቡ በመገደዳቸው ኑሮን የከፋ ቢያደርግባቸውም፣ አማራጭ ስለሌላቸው ከልጆቻቸው የትምህርት ቤት ክፍያ፣ ከቤት ኪራይና ከቀለባቸው አብቃቅተው መቆጠቡን ተያይዘውታል፡፡ ቀደም ብሎ ከዘጠኝ ዓመታት በፊት የተመዘገቡ ነዋሪዎች አስተዳደሩ በቅርቡ በዕጣ እንደሚያከፋፍል ቃል የገባውን የጋራ መኖሪያ ቤት እየጠበቁ ቢሆንም፣ አስተዳደሩ ግን ቃሉን አልጠበቀም፡፡

በዳግም ምዝገባው (ከሐምሌ እስከ ነሐሴ 2005 ዓ.ም.) ለነባር ተመዝጋቢዎች ከ17 ሺሕ በላይ የጋራ መኖሪያ ቤቶች በዕጣ እንደሚከፋፈሉ፣ በድጋሚ በሚያዝያ ወር 2006 ዓ.ም. እንደሚያከፋፍል የተናገረውን ቃል በማጠፍ፣ ዕጣው የሚወጣው በሰኔ ወር ነው በማለቱ ነዋሪዎች ‹‹ድሮም እነሱን ማመን›› በማለት ቅሬታቸውን በተለያዩ አጋጣሚዎች እየገለጹ ይገኛሉ፡፡ ሌላው አስተዳደሩ በልማት ምክንያት ለሚነሱ ነዋሪዎች የኮንዶሚኒየም ቤት ለመስጠት ቃል የገባ ቢሆንም፣ የኮንዶሚኒየም ቤቶች ግንባታ ባለመጠናቀቁ በዕቅዱ መሠረት እየሄደ አለመሆኑን የከንቲባው ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ አሰግድ አምነዋል፡፡

በመሀል ከተማ በሚገኙ ቦታዎች ላይ ይገነባሉ በሚል በ40/60 ፕሮግራም የበርካታ ቤት ፈላጊዎችን ቀልብ ለመሳብ ፈልጐ የነበረው አስተዳደሩ፣ ያሰበውን ያህል ተመዝጋቢ ባለማግኘቱ በአራት ሳይቶች ላይ እየገነባ ከመሆኑ ባለፈ ብዙም የተሳካ ነገር ሲያደርግ አይስተዋልም፡፡ አዋጭነቱም ጥያቄ ውስጥ የሚገባ በመሆኑ የ40/60 ተመዝጋቢዎች በማኅበር ከተደራጁት ውስጥ  እንዲካተቱ የተለያዩ ዘዴዎችን በመጠቀም ግፊት እያደረገ መሆኑም ይሰማል፡፡ በማኅበር ተደራጅቶና መሬት ወስዶ ለመሥራት የተጀመረው ፕሮግራምም የተፈለገውን ያህል እንደልሆነ እየተነገረ ነው፡፡ በአጠቃላይ አስተዳደሩ በቤቶች ልማት ፕሮግራም ላይ እያደረገ ባለው እንቅስቃሴ ባለፉት ስድስት ወራት ከወረቀት ላይ ያለፈ አርኪ ሥራ አለመሥራቱን ያመለክታል፡፡

<em><strong>የቴሌኮምና የኤሌክትሪክ መቆራረጥ</strong></em>

ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በአዲስ አበባ ከተማ ውስጥ የቴሌኮምና የኤሌክትሪክ ኃይል መቆራረጥ የከፋ ደረጃ ላይ ደርሷል፡፡ ኤሌክትሪክ በተደረጋሚ ከመቆራረጡም በላይ በአንዳንድ አካባቢዎች ላይ ለቀናት እየጠፋ መሆኑ የኅብረተሰቡ የዕለት ከዕለት ችግር ሆኗል፡፡

ኤሌክትሪክ በሚቆራረጥበት ወቅት ውኃና የቴሌኮም ኔትወርክ አብረው የሚቋረጡ በመሆናቸው ኅብረተሰቡ ለከፋ ቀውስ እየተጋለጠ ይገኛል፡፡ የኤሌክትሪክ መቆራረጥ በማይኖርበት ወቅት ጭምር ውኃና ቴሌኮም የሚቋረጡ በመሆናቸውም ችግሩን አባብሶታል፡፡

ይህንን ችግር የከተማው ነዋሪዎች በሰፊው የሚያነሱት በመሆኑ፣ አስተዳደሩ ከሁለቱ የፌዴራል መንግሥት መሥሪያ ቤቶች ጋር በጋራ ለመሥራት ኮሚቴ አዋቅሯል፡፡

ከንቲባ ድሪባ ኩማ ባቀረቡት የስድስት ወራት የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት ይህንን ጉዳይ ጠቅሰዋል፡፡ የከንቲባው ሪፖርት እንደሚለው በኤሌክትሪክና በቴሌኮም ላይ የሚስተዋሉ የአገልግሎት አሰጣጥ ችግሮችን ለመፍታት ሥራዎች እየተሠሩ ይገኛሉ፡፡

የመጀመርያው የከተማው መልሶ ማልማትና ግዙፍ የልማት እንቅስቃሴ በሚካሄዱባቸው አካባቢዎች የመሠረተ ልማት (ኤሌክትሪክ፣ ውኃና ቴሌኮም) መስመሮች ለጉዳት ተዳርገዋል፡፡

እነዚህን ችግሮች ለመፍታት ከሁለቱ ተቋሞች ጋር የጋራ ሥራ መጀመሩ፣ ከዓለም አቀፍ ተሞክሮ (ቤንች ማርክ) በመነሳት የተለያዩ የማሻሻያ ሥራዎች እየተሠሩ መሆኑ በሪፖርቱ ተጠቅሷል፡፡

የከንቲባው ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ አሰግድ እንደገለጹት በየ15 ቀኑ በጋራ መድረኩ ውይይት ይደረጋል፡፡ እስካሁን ድረስ የቴሌኮም ችግርን ለመፍታት በ400 ቦታዎች ላይ የቴሌኮም አንቴናዎች መትከያ ያስፈልጋል ተብሎ፣ 327 ቦታዎችን አስተዳደሩ መስጠቱንና ቀሪዎቹ በሕንፃዎች አናት ላይ የሚተከሉ በመሆናቸው ኢትዮ ቴሌኮም ከሕንፃ ባለቤቶች ጋር እየተነጋገረበት መሆኑ ተወስቷል፡፡

የኤሌክትሪክ መቆራረጥን ለማስቀረትም የኤሌክትሪክ መስመሮችና ማስፋፊያ ጣቢያዎችን አቅም ለማሳደግ የሚያስችሉ ሥራዎች እየተሠሩ መሆኑን አቶ አሰግድ አክለዋል፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በኢኮኖሚያዊና በማኅበራዊ ዘርፎች በርካታ ቅሬታዎች እየቀረቡበት ይገኛሉ፡፡ የኅብረተሰቡን ቅሬታ መሠረት በማድረግ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ለመፍታት፣ በየወሩ ከኅብረተሰቡ ጋር የሚገናኝበትን አሠራር ከታህሳስ 15 ቀን 2005 ዓ.ም. ጀምሮ መዘርጋቱን አስታውቆ ነበር፡፡

በዚህ መድረክ በየጊዜው ኅብረተሰቡ በርካታ አንገብጋቢ ጥያቄዎችን ያለማቋረጥ ከማንሳቱም በላይ፣ የአስተዳደሩ ከፍተኛ ባለሥልጣናት ችግሩን ከመሠረቱ ለማድረቅ እየሠሩ መሆናቸውን ከመናገር አልተቆጠቡም፡፡

ነገር ግን ከጥቃቅን እስከ ትላልቅ የሚነሱት ችግሮች ከመፍታት ይልቅ ይበልጥ እየተተበተቡ መሄዳቸውን በተለያዩ መድረኮች እየተገለጹ ነው፡፡ በዚህም የከተማው ነዋሪዎች እርካታ እንዲያገኙ ማድረግ አልተቻለም፡፡

ነዋሪዎች እንደሚሉት ለችግሮቹ ሁሉ ቁልፍ የሆነው የአስተዳደሩ ከፍተኛ አመራሮች በባለቤትነት ስሜት ሥራዎችን መሥራት አለመቻላቸው፣ ከአቶ ኩማ ጋር የከረመው አሮጌው ካቢኔ እንዳለ ሳይነካ ከአቶ ድሪባ ጋር እንዲቀጥል መደረጉ በምክንያትነት እየተጠቀሰ ነው፡፡ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በበርካታ ችግሮች የተተበተበ በመሆኑ መዋቅራዊ ለውጥና በሙያ የበለፀገ የሰው ኃይል ሥምሪት ወሳኝ መሆኑን ነዋሪዎች በአፅንኦት ይገልጻሉ፡፡
<div></div>
</div>

Hiber Radio: ገዢው ፓርቲ ለመጪው ምርጫ በሚል ደጋፊዎቼ ያላቸውን በብድር ስም ገንዘብ መስጠት ጀመረ

$
0
0

ጋዜጠኛ ሃብታሙ አሰፋ

ጋዜጠኛ ሃብታሙ አሰፋ

የህብር ሬዲዮ መጋቢት 21  ቀን 2006 ፕሮግራም

 <…ገዢው ፓርቲ በጎንደር ብቻ ሳይሆን በተለያዩ አካባቢዎችም   ለሶስት ዓመት ብድር ውሰዱ እያለ ገንዘብ እየረጨ ነው። ይሄን በጥንቃቄ እየተከታተልን  ነው .. . ሰሞኑን ከአምቦ የተፈናቀሉት ዜጎች ጉዳይ የሁሉም ዜጋ የነገ ህልውና ጉዳይ ነው…  >

አቶ ዳንኤል ተፈራ የአንድነት የድርጅት  በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ተጠይቀው ለህብር ከሰጡት ማብራሪያ የተወሰደ(ሙሉውን ያዳምጡት)

ዓለም አቀፉ የሰብዓዊ መብት ድርጅት _ዩማን ራይትስ ዎች በኢትዮጵአውያን ላይ የህወሃት አገዛዝ ተቃዋሚዎቼ ባላቸው ላይ እያደረገ ያለውን ስለላና የመብት ረገጣ አስመልክቶ ያወጣው ሪፖርት ቅኝት   (ልዩ ዘገባ)

ሺሻ የሚያስከትለው የጤና መዘዝ ከወሲብ ስንፈት እስከ ጽንስ መቋረጥ የሚያስከትላቸው የጤና ስጋቶች  (ወቅታዊ ዘገባ)

ከዓመት በፊት ለስራ ማቆም አድማ የወጡት የቬጋስ ኢትዮጵአውያንና ኤርትራውያን አሽከርካሪዎች በተመለከተ

የኢሳት የቬጋስ ገቢ ማሰባሰቢያ ዝግጅትን የተመለከተ ቃለ መጠይቅ

ሌሎችም ዝግጅቶች

ዜናዎቻችን

ሕዝቡ የስርዓተን ለፖለቲካ ጠቀሜታ ሲባል እርስ በእርሰ እየተፋጀ እንዲቀጥል የሚደረገውን ሴራ በቃ ብሎ መነሳት አለበት

ገዢው ፓርቲ ለመጪው ምርጫ በሚል ደጋፊዎቼ ያላቸውን በብድር ስም ገንዘብ መስጠት ጀመረ

ኢትዮጵያዊው አርሶ አደር ለንደን ውስጥ የእንግሊዝ መንግስትን ለመክሰስ የሕግ እርዳታ አገኙ

የአረና ሊቀመንበር ትግራይ ውስጥ ለስብሰባ ቅስቀሳ እንደወጡ መታሰራቸው ተሰማ

የታሰሩ የሙስሊሙ መሪዎችን ከአገዛዙ ጋር ለማስታረቅ የሞከረው የበድር ኢንተርናሽናል ሽምግልና አለመሳካቱ ተገለጸ

የታሰሩት የሙስሊሙ ተወካዮች አንድም ጥያቄ አልተቀበሉትም

በጋምቤላ በ1993 በህወሃት የተፈጸመውን የዘር ማጥፋት ወንጀል በመቃወም ከአገር የወጡት የቀድሞው የክልሉ ፕ/ት ደበብ ሱዳን ላይ ታስረዋል ተባለ

የግብጹ ፓትርያርክ የአባይ ግድብ ካይሮን ይጎዳል ሲሉ ቅሬታቸውንና ተቃውሟቸውን ገለጹ

የየመን የጸጥታ ሀይሎች 21 የታገቱ ኢትዮጵያውያን ስደተኖችን አስለቀቁ

ኢትዮጵያዊው የአካል ጉዳተኛ የዓለምን ክብረ ወሰን ሰበረ

ሌሎችም ዜናዎች አሉ

በ ሱዳን ሀገር ውስጥ በኢትዮጽያዊያኖች ላይ ቤት ለቤት አፈሳ

የአንድነት ፓርቲ የሰሜን ቀጠና ኃላፊ በደሴ ከተማ ተደበደቡ

$
0
0

ፍኖተ ነፃነት

Aemero

የአንድነት ፓርቲ የሰሜን ቀጠና ኃላፊ አቶ አዕምሮ አወቀ

በደሴ ከተማ የሚደረገው ሰላማዊ ሰልፍ ለማስተባበር ወደ ስፍራው የተጓዙት የአንድነት ፓርቲ የሰሜን ቀጠና ኃላፊ አቶ አዕምሮ አወቀ ድብደባና ዝርፊያ እንደተፈፀመባቸው ለፍኖተ ነፃነት አስታወቁ፡፡

ዓርብ መጋቢት 19 ቀን 2006 ዓ.ም ከምሽቱ 1፡15 ላይ በደሴ ከተማ በተለምዶ ቶታል ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ዕራት በልተው ሲወጡ ታርጋ የሌለውና መስታወቱ ጥቁር በሆነ ኮብራ መኪና አጠገባቸው መጥቶ ሲቆም ከውጪ ሁለት ሰዎች ገፍተው ወደ መኪናው እንዳስገቡአቸው ጨምረው አስረድተዋል፡፡ በመቀጠልም አፍና አፍንጫቸው ላይ ለጊዜው ምንነቱ ያልታወቀ ፈሳሽ ነገር ከነፉባቸው በኋላ መኪናው ተዘግተው ድብደባ ፈጸመውባቸዋል፡፡ እሳቸውም ድብደባውን ሲከላከሉና የመኪናውን መስታወት ለመስበር ሲታገሉ ደብዳቢዎቹ ከኪሳቸው ውስጥ 1735 ብር፣ የነዋሪነት መታወቂያ፣ የፓርቲው የብሔራዊ ምክር ቤት መታወቂያ ወስደው ከመኪናው ገፍትረው እንደጣሏቸው ገልጸውልናል፡፡ -

ቴዲ አፍሮ በጊዮን ሆቴል ለዳግማ ትንሣኤ ለሚያቀርበው ኮንሰርት 1.2 ሚሊዮን ብር ተከፈለው

$
0
0

teddy afro
(ዘ-ሐበሻ) የዳግማ ትንሣኤን በዓል በማስመልከት በአዲስ አበባ ጊዮን ሆቴል የሙዚቃ ኮንሰርቱን የሚያቀርበው ቴዲ አፍሮ 1.2 ሚሊዮን ብር እንደተከፈለው የቅርብ ምንጮች ለዘ-ሐበሻ ገለጹ።

በቅርቡ ሱዳን ካርቱም 2 የተሳኩ የሙዚቃ ኮንሰርቶችን አቅርቦ ወደ ኢትዮጵያ የተመለሰው ቴዲ አፍሮ የዶን አርትና ፕሮሞሽን፣ ኤቢሲ ትሬዲንግ፣ ጄ አር የሙዚቃ ፕሮዳክሽን እና ኤ ፕላስ ኤቨንትስ የተሰኙት ድርጅቶች በጋራ ባስተባበሩት የጊዮን ሆቴሉ የሙዚቃ ኮንሰርት ለቴዲ የተከፈለው ገንዘብ ድምጻዊውን ከኢትዮጵያ ድምጻውያን ብቸኛው ተከፋይ ሆኖ እንዲቀጥል አስችሎታል።

ኤፕሪል 26 ቀን 2014 ወይም በኢትዮጵያ አቆጣጠር ሚያዝያ 18 ቀን 2006 ዓ.ም በሚደረገው ይኸው የጊዮን ሆቴሉ የቴዲ ኮንሰርት የመግቢያ ዋጋው ስንት እንደሚሆን ከምንጮቻችን ያገኘነው መረጃ ባይኖርም በጉጉት እየተጠበቀ መሆኑ ግን በከተማው በሰፊው ይወራል።

ቴዲ አፍሮ “ወደ ፍቅር ጉዞ” በሚል በጊዮን ዝግጅቱን ካቀረበ በኋላ በሰሜን አሜሪካና በአውሮፓ ሌሎች ዝግጅቶችን ለማቅረብ እንደሚንቀሳቀስ ጨምሮ የደረሰን መረጃ ያመለክታል።

ኢህአዲግ/ወያኔ ሕዝብ ለማፋጀት የገነባውን ‘የመርዝ ብልቃጥ’በያዝነው ሳምንት በሃያ ሚልዮን ብር ወጪ ይመርቃል

$
0
0

ምርቃቱ የሩዋንዳው የዘር ማጥፋት ግጭት ከተጀመረበት 20ኛ ዓመት ጋር ገጥሟል።ባጋጣሚ ወይስ ታስቦበት?

ጉዳያችን
መጋቢት 22/2006 ዓም

ኢትዮጵያን እየመራ የሚገኘው ኢህአዲግ/ወያኔ የኢትዮጵያን ሕዝብ ከቀን ወደ ቀን እርስ በርሱ እንዳይተማመን፣እንዲነቃቀፍ፣እንዲጠራጠር ከእዚህ ባለፈ ደግሞ ግጭት እንዲፈጠር እያደረገ 22 ዓመታትን ዘለቀ።ህዝቡ እለት ከእለት በገዢው መንግስት የሚወጠኑለትን የእርስ በርስ ማጋጫ ተንኮሎች እየተመለከተ ልቦናው በእጅጉ እየደማ ነው።

አንድ ወራሪ የውጭ ጠላት ሊሰራ የሚችለውን ያህል ህዝብን ከሕዝብ ጋር የማጋጨት ሥራ ኢህአዲግ/ወያኔ በትክክል ሰርቶበታል። የሃገሪቱን ፌድራል አስተዳደር በየትኛውም ዓለም ያልታየ ቋንቋን መሰረት ያደረገ አስተዳደር ለኢትዮጵያ ደገሰላት።ፌድራላዊ አስተዳደር በዘመናዊው ዓለም አንዱ እና አማራጭ የአስተዳደር ዘይቤ ይሁን እንጂ በየትኛውም ሀገር መሰረት የሚያደርገው የመልክዓ ምድርን አቀማመጥ እና ታሪካዊ አሰፋፈርን ነው። እርግጥ ነው ጣልያን ሀገራችንን በወረረ ዘመን አሁን ወያኔ የሚጠቀምበትን የክልል አስተዳደር የመሰለ ቋንቋን መሰረት ያደረገ የአስተዳደር መዋቅር ዘርግቶ ነበር።

አንዳንዶች የአሁኑ ቋንቋን መሰረት ያደረገ አስተዳደር የብሔር ብሄረሰቦችን መብት ከማስከበር አንፃር የሚመስላቸው የዋሃን አይጠፉም።ግን ፈፅሞ አላማው ይህ ላለመሆኑ ብዙ ማስረጃ መጥቀስ ይቻላል።እርግጥ ነው የህዝብ ባህል ማለትም ቋንቋው፣አለባበሱ፣ታሪኩ ወዘተ ሊጠበቅለት እና ከለላ ማግኘት አለበት።ይህ ከለላ በማግኘት መብት  ስም ወንጀል ሲሰራ፣ቁርሾ በባትሪ እየተፈለገ ሲራገብ እና ሕዝብን ከሕዝብ ለማጋጨት ሲውል ነው ወንጀሉ።

ኢህአዲግ/ወያኔ ሕዝብ እርስ በርሱ በጎሳ ሲጋጭ መፍትሄ ለመፈለግ ከመነሳት ይልቅ ጉዳዩን ሲያባብስ እና ቤንዚን ስያርከፈክፍ ማየት ለኢትዮጵያ ሕዝብ ዕለት ከዕለት የሚመለከተው ድራማ ሆኗል። ለእዚህም ብዙ አብነቶችን መጥቀስ ይቻላል። ለእዚህ ፅሁፍ ግን ሁለት ምሳሌዎችን እንጥቀስ -

1/  በዩንቨርስቲዎች ውስጥ ወጣቶች ‘አንተ የእገሌ ነህ አንተ የእንቶኔ ነህ’ ተባብለው ፀብ ሲነሳ ጉዳዩ የመጪው ትውልድ እና የአሁኑ ትውልድ አደገኛ አቅጣጫ ነው ብሎ የችግሩን ስር ለመፍታት ከመጣር እና የጉዳዩን አስከፊነት  በመገናኛ ብዙሃን ከመግለፅ እና ከማስተማር ይልቅ ፖሊስ ይልቁን ከአንድኛው ወገን ቆሞ ሌላውን ሲያስር እና ሲቀጣ መመልከት ዘግናኝ ተግባር ነው።

2/ ሕዝብ ለዘመናት ከኖረበት የእርሻ ቦታ ”የእገሌ ዘር ነህ” ተብሎ በክልል መስተዳድሮች ጭምር ሲባረር ለጉዳዩ እንደ መንግስትነት ለመዳኘት ሳይሆን የሚሞከረው እንደ ቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ መለስ አባባል ”ቀድመው ባልተወለዱበት ሀገር መስፈር የለባቸውም” እንደ አቶ አለምነህ የብአዴን ቢሮ ምክትል ኃላፊ ደግሞ ”የትዕቢት ልጋግ” ነው የሚሉ መልሶችን መስማት እራስ ያማል።መሪዎቻችን እንዲህ እያሉ ከጉርዳፈርዳ እስከ አሶሳ፣ከአሶሳ እስከ ሐረር፣ ከሐረር እስከ ጅጅጋ፣ ከጅጅጋ እስከ ቦረና ጉጂ፣ ድረስ በብዙ አስር ሺህ የሚሆኑ ኢትዮጵያውያን በኢህአዲግ/ወያኔ የጎሳ ፖለቲካ ተሰደዱ፣ተገደሉ።ይህ ሁሉ ሲሆን ግን መንግስት ጉዳዩን እንደ ትልቅ ችግር ሳይሆን እንደ አንድ የማስተዳደርያ ዘዴ እንደቆጠረው በ እርግጠኝነት መረዳት ይቻላል።

በያዝነው ሳምንት  በሃያ ሚልዮን ብር ወጪ የሚመረቀው የመርዝ ብልቃጥ 

Arsi Oleno

በአርሲ ዞን በሂቶሳ ወረዳ ከሃያ ሚልዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ ያሰራውን  ”አኖሌ ሐውልት” እና ሙዝዬም

የእርስ በርስ ግጭቶች ከትውልድ ወደ ትውልድ እንዲሻገሩ የሚጥረው ኢህአዲግ/ ወያኔ ለእርስ በርስ ጦርነቶች እየመረጠ ሃውልት ሲሰራ ከርሞ በእዚህ ሳምንት ደግሞ ለየት ያለ የጥፋት ድግስ የሚሆን ከመቶ አመታት በፊት ለመፈፀሙ ምንም አይነት የታሪክ ማስረጃ የሌለው በዳግማዊ ምኒልክ ዘመን በአርሲ ዞን በሂቶሳ ወረዳ ተፈፅሟል ያለውን የታሪክ ምሁራን ያላረጋገጡትን የፈጠራ ታሪክ ከሃያ ሚልዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ ያሰራውን  ”አኖሌ ሐውልት” እና ሙዝዬም  በእዚህ በያዝነው ሳምንት እንደሚመረቅ ኢቲቪ ዛሬ መጋቢት 22/2006 ዓም የዜና እወጃው ላይ አስታወቀ።የፈጠራው ታሪክ ከመቶ ዓመታት በፊት የአፄ ምኒልክ ሰራዊት የኦሮሞ ሴቶችን ጡት ቆርጦ ነበር እና ማስታወሻነቱ ለተቆረጡት ጡት እና እጅ ይሁን” ይላል የሃውልቱ የመሰራት ምክንያትን ኦህዴድ /ኢህአዲግ/ወያኔ ሲናገር። አሳዛኝ የደረስንበት የዝቅጠት ዘመን።በየትኛውም ሀገር ውስጥ በቀደሙ መሪዎች ያውም ከመቶ አመታት በላይ ለሆነው ታሪክ ቀርቶ የቅርቦቹም ቢሆን ለተሰሩ ተገቢ ያልሆኑ ድርጊቶች ለመጪው ትውልድ የሚያቆይ የእልቂት ድግስ ከፋች ሃውልት አይሰራም። የሚጠጣ ውሃ፣ የምበላው ምግብ ለሌለው ሕዝብከ 20 ሚልዮን ብር በላይ አውጥቶ መበተን ምን የሚሉት ፈልጥ ነው?

አንድ መንግስት ሕዝብ ከህዝብ ጋር አብሮ የሚኖርበትን ዘዴ ሲቀይስ ልዩነትን እያጎላ ሳይሆን አንድነትን እያሳየ እና እያጎላ ሕዝብ በፍቅር እና በስምምነት እንዲኖር ይጥራል እንጂ እንዴት ከአሁኑ ትውልድ አልፎ ለመጪው ትውልድ ቂም ለማውረስ ተግቶ ይሰራል? ይህ ተግባር ማንን ይጠቅማል? ለመሆኑ ያለፉ ነገስታት በወቅቱ በነበረው የቅጣት መንገዳቸው ሁሉ የቀጡትን የቅጣት አይነት እየዘረዘርን ሃውልት ብንሰራ የቱን ከየቱ እንመርጣለን?

የሃውልቱ ምርቃት እንደ ትልቅ የሀገር ልማት ዛሬ ኢቲቪ ቀድሞ ዛሬ ይናገረው እንጂ ወቅቱ የሩዋንዳው እልቂት የተጀመረበት 20ኛ አመት ጋር ገጥሟል።በሚያዝያ 7/1994 ዓም  እስከ ሐምሌ/1994 ዓም እ ኤ አቆጣጠር የቆየው በቱትሲዎች እና በሁቶዎች መካከል የተደረገው እልቂት ከአምስት መቶ ሺህ በላይ ሕዝብ ሕይወት ቀጥፏል።የሩዋንዳው እልቂት በአንድ ሌሊት ድንገት የደረሰ ጉዳይ አይደለም።በሂደት አልፎ አልፎ በተነሱ ቁርሾዎች ጥርቅም ሳብያ መሆኑን መዘንጋት አይገባም።የዛሬ የባለ ሃያ ሚልዮን ሃውልት ገንቢዎችም ሆኑ አስገንቢዎች መዘንጋት የሌለባቸው  በሰሩት ሥራ ሁሉ የሚጠየቁበት ቀን እንደሚመጣ መጠራጠር አይገባም።የመርዝ ብልቃጡም ይሰበራል የፍርድ ቀኑም ይቆረጣል።

ጉዳያች-gudayachn.blogspot.com/
መጋቢት 22/2006 ዓም


”የሃይማኖቴን ጠላት ወርውሬ ባልገድል ሞቼ ፈጣሪዬ በደሜ ይበቀልልኝ ” ሰማዕቱ አቡነ አቡነ ጴጥሮስ (ቪድዮ)

ሞቴ ተሰውሮ –ከዶ/ር ፍቅሬ ቶለሳ

$
0
0

ዶ/ር ፍቅሬ ቶለሳ

ዶ/ር ፍቅሬ ቶለሳ


ሞቴ ተሰውሮ የሰረስረኛል፣
በያንዳንዱ ዕለት ይሽረረሽረኛል፣
ገንብቶ አሳምሮ ደግሞ ያፈርሰኛል፣
ሾሞ ከፍ አድርጎ ደግሞ ይሽረኛል።

ሙሉውን ለማንበብ እዚህ ይጫኑ

ነጻ መብራት፣ ስልክ እና ውሃ በካሳ መልክ ሊሰጥ ነው (ዳዊት ከበደ ወየሳ)

$
0
0
(ዳዊት ከበደ ወየሳ) 
በመብራት መቆራረጥ የሚሰቃየው የኢትዮጵያ ህዝብ “እፎይ” የሚልበትን ቀን ሁሉም ይናፍቃል። የአባይ ወንዝ ከተገደበ በኋላ የሚመነጨው የኤሌክትሪክ ሃይል ከኢትዮጵያ አልፎ ለሱዳን እና ለግብጽ እንደሚበቃም ይነገራል። ከዚህ ግድብ በተጨማሪ የግልገል ጊቤ 2 እና 3 ፕሮጀክት ሲጠናቀቅ ኢትዮጵያ የሚኖራት የመብራት ሃይል በአስር እጥፍ እንደሚጨምር የዘርፉ ሙያተኞች ይመሰክራሉ።
በዚህ አጋጣሚም በመብራት መቆራረጥ እና እጦት የሚሰቃየውም ህዝብ የሚካስበት አጋጣሚ ይፈጠራል። መብራት ሃይል ዛሬ ያወጣው መግለጫ እንዳረጋገጠው ከሆነ፤ “እስካሁን መብራት ያጣውን የኢትዮጵያ ህዝብ ነጻ የኤሌክትሪክ ሃይል ወይም ግምቱ ታውቆ በጥሬ ገንዘብ ካሳ ይከፈለዋል።” ተብሏል። የቴሌኮምዩኒኬሽንም በበኩሉ የመብራት ሃይልን ተነሳሽነት አድንቆ በቴሌም በኩል እስካሁን በኔት ዎርክ መቆራረጥ ሲሰቃይ የነበረውን ህዝብ ለመካስ፤ በኢትዮጵያ የሚሰራውን “አባ ዱላ” የሚል ስያሜ የተሰጠውን የስልክ ቀፎ ለደንበኞቹ በነጻ እንደሚሰጥ ወይም ከመቶ እስከ 1ሺህ ብር ዋጋ የሚያወጡ ሲም ካርዶችን የሚያድል መሆኑን አሳውቋል።
የመብራት ሃይል እና የቴሌን ካሳ አከፋፈል ያደነቀው የውሃ ሃብት ልማት በበኩሉ በሸገር ሬድዮ ሰበር ዜና አሰምቷል። ሰበር ዜናውን ያነበበው አለምነህ ዋሴ ሲሆን፤ “አስደሳች ዜና ለውሃ አፍቃሪዎች” በማለት ነበር ዜናውን የጀመረው። በመቀጠልም… የውሃ እና ሃብት ልማት ሚንስቴር ዛሬ እንዳስታወቀው ከሆነ፤ “በቅርቡ ውሃን በፕላስቲክ እየሞላን የመሸጥ ፈቃድ ከፌዴራሉ መንግስት ተቀብለን ስራችንን ለመጀመር በዝግጅት ላይ ነበርን። የገፈርሳ የአባ ሳሙኤል እና የቀበና ውሃዎችን እያጣራን ለህዝቡ ጓዳው ድረስ በቧንቧ አቅርበንለታል። አሁን ግን የመብራት እና የቴሌን ፈለግ በመከተል ህዝቡን ለመካስ ተነስተናል። አባይ ይገደባል፣ ህዝቡም ነጻ ውሃ ያገኛል።” ብለዋል። በዚህም መሰረት የውሃ እና ሃብት ልማት በቅርቡ እያሸገ የሚሸጣቸውን የፕላስቲክ ውሃዎች ለደንበኞቹ በነጻ የሚሰጥ መሆኑን ገልጾ፤ ይህንን የሚያስተባብሩ እና የሚያድሉ ሰራተኞቹ ወደ መንደሮች እና ኮንዶሚኒየሞች ሲመጡ፤ ህብረተሰቡ አንድ ለአምስት በመሆን አስፈላጊው ትብብር እንዲያደርግላቸው የባለልጣኑ መስሪያ ቤት አደራ ብሏል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ፤ “ወንዞች ይገደቡ ይዋሉ ለልማት” በሚለው የድሮ የደርግ ዜማ በመታጀብ ዜናውን ለህዝብ አቅርቦ የነበረው ሰይፉ ፋንታሁን ባልታወቁ ታጣቂዎች መታገቱ የ-ኢትዮፒሊንካ አዘጋጅ የሆነው ብርሃኔ ለዝግጅት ክፍላችን ገልጿል። እንደብርሃኔ አባባል ከሆነ፤ “ሰይፉን ያገቱት… ይህን የመሰለ ዜና… እንዴት በደርግ ዜማ አጅበህ አቀረብክ በማለት ነው። እንደአሰራር የሰይፉን ድርጊት ብንቃወምም የአጋቾቹን ድርጊት ግን አጥብቀን አውቅዘናል። ይህንንም ድርጊት በመቃወም ለጠቅላይ ሚንስትሩ ቢሮ ደብዳቤ ጽፈናል።” ብሏል።
እኛም ዜናችንን ከማጠናቀቃችን በፊት “እንኳን ለዛሬው April Fool በሰላም እና ጤና አደረሳቹህ እንላለን።” ከላይ በApril Fool ስም ዜናውን እናቅርብ እንጂ እውነት ይህ ህዝብ በአንድም ሆነ በሌላ መንገድ መካስ እንዳለበት እናምናለን።

ሕወሓት በምርጫ 2007 በትግራይ ክልል ሊሸነፍ እንደሚችል አመነ

$
0
0

አብርሃ ደስታ ከመቀሌ

Arena-Tigray-logoዓረና ፓርቲ በትግራይ ክልል ወረዳዎች በመዘዋውር ባሰብሰበው መረጃ መሰረት በ2007 በሚደረገው ሀገራዊ ምርጫ ገዥው ፓርቲ የህዝብን ድምፅ ካከበረ ህወሓት በመላው ትግራይ ሙሉ በሙሉ ይሸነፋል። አንድ የህወሓት የስራ አስፈፃሚ አባል (ለግዜው ስሙ ይቅር) በዓዲግራት ከተማ ለተሰበሰቡ ከምስራቃዊ ዞን የተውጣጡ የህወሓት ካድሬዎች “እናንተ በምትፈፅሙት በደል ምክንያት በ2007 ምርጫ እንሸነፋለን። ግን አንዳንድ የምናደርጋቸው ነገሮች ስለሚኖሩ ሙሉ በሙሉ ተስፋ አትቁረጡ። ለራሳችሁ ዕጣ ፈንታ ስትሉ በደንብ ስሩ” ማለቱ ታውቋል። ካድሬዎቹም “በናንተ (የላይኞቹ አመራሮች) ችግር ነው የምንሸነፈው፤ ህዝብ የማይቀበለውን ነገር እንድናሳምን ታስገድዱናላቹ” የሚል መልስ በመስጠታቸው የእርስበርስ ንትርክ መከፈቱ ታውቋል። ከስብሰባው በኋላ ካድሬዎቹ የንትርኩ ነጥቦች ለዓረና አባላት አስረድተዋል።

በዓረና እንቅስቃሴ የሰጉ የህወሓት መሪዎች ህዝብን በገንዘብ መደለል ጀምረዋል። ባሁኑ ግዜ የትግራይ ህዝብ በህወሓቶች በሦስት ደረጃዎች ተከፍሎ ግሬድ ተሰጥቶታል። ግሬድ A, B ና C። ግሬድ “A” ታማኝ የህወሓት ካድሬ፣ ግሬድ “B” መሓል ሰፋሪ፣ ግሬድ “C” ተቃዋሚ (ዓረና)። በዚሁ መሰረት ህወሓትን ለማገልገል ፍቃደኛ የሆነ ሰው (ታማኝ ካድሬ A) ለስብሰባ ይጠራና የማዳበርያን ዕዳ ለመክፈል የሚያግዘው 3000 ብር የውሎ አበል ተብሎ ይሰጠዋል። 3000 ብር ከተቀበለ በኋላ ተቃዋሚዎችን ይታገላል፣ ህወሓት እንዲመረጥ ያግዛል፣ ታማኝ የህወሓት አገልጋይ ይሆናል። ለህወሓት ታማኝ ያልሆነ ለስብሰባ አይጠራም፤ ገንዘብም አይሰጠውም። በ3000 ብር የምርጫ ድምፅ መግዛት ይሉታል እንዲህ ነው። የምርጫ ድምፅ እየተገዛበት ያለ ገንዘብ የህወሓት ሳይሆን በግብር መልክ የተሰበሰበ የመንግስት ገንዘብ ነው። መንግስት ብር አነሰኝ እያለ ግብር እየጨመረ ነጋዴዎች ንግዳቸውን ይዘጋሉ። ህወሓቶች ደግሞ የሰበሰቡትን ገንዘብ ለምርጫ ጅንጀና ይጠቀሙታል።

(ከዚህ ቀደም የአረናን ሕዝባዊ ስብሰባ እንዳይሳተፉ የተከለከሉ የሽሬ ነዋሪዎች - ፎቶ ከአብርሃ ደስታ) - ፎቶ ፋይል

(ከዚህ ቀደም የአረናን ሕዝባዊ ስብሰባ እንዳይሳተፉ የተከለከሉ የሽሬ ነዋሪዎች – ፎቶ ከአብርሃ ደስታ) – ፎቶ ፋይል

የትግራይ አርሶአደሮች እንደዚህ በፖለቲካ ታማኝነት በዉሎ አበል መልክ ገንዘብ እየተሰጣቸው የማዳበርያ ዕዳቸውን መክፈል ከቻሉ ጥሩ ነው። ባንዳንድ አከባቢዎች ግን የዉሎ አበሉ መጠን ይለያያል። ለምሳሌ በደቡባዊ ምስራቅ ዞን ለየት ያለ አጋጣሚ ተፈጥሯል። ህወሓቶች በሁሉም ዞኖች እንደሚያደርጉት ሁሉ ታማኝ የተባሉ (ለምርጫ ሊያገለግሉ የሚችሉ) 200 የሳምረ አርሶአደሮች መለመሉ። አርሶአደሮቹ ሲመለመሉ “ለስብሰባ ትሄዳላቹ፣ 3000 ብር አበል ይሰጣችኋል፤ ስለዚህ 3000 ብሩን ለማግኘት በመጪው ሰኔ ላይ ለምትወስዱት ማዳበርያ 1200 ብር አሁን ክፈሉ” ይሏቸዋል። አርሶአደሮቹም 3000 ብሩን ለማግኘት 1200 ብር እንደምንም ብለው ከፈሉ። ከሳምረ ለስብሰባ ተብሎ ወደ ሕዋነ ተወሰዱ፤ ፖለቲካ ተጀነጀኑ። በመጨረሻ እነሱ 3000 ብር እየጠበቁ 640 ብር ብቻ እንደሚሰጣቸው ተነገራቸው። ከ640 ም 600 ው መቆጠብ አለባቹ በሚል ሰበብ በህወሓቶች እጅ ሲቀር 40 ብር ብቻ ለትራንስፖርት ተሰጣቸው። አርሶአደሮቹ አሁን ቅሬታቸው አካፍለውናል።

አዎ! የህዝብ ድምፅ ከተከበረ ዓረና ሙሉ በሙሉ ያሸንፋል። እናም ህወሓቶች በሰለማዊ መንገድ ስልጣን ያስረክባል። የህወሓት ካድሬዎችም መብታቸው ተጠብቆላቸው በሰላም በሀገራቸው ይኖራሉ። ከፈለጉ በመንግስት መስራቤት በሙያቸው ተቀጥረው ይሰራሉ፣ ወይም ህወሓት ተቃዋሚ ፓርቲ አድርገው ለሚቀጥለው ምርጫ ለመወዳደርና ለማሸነፍ ይሞክራሉ። በሰለማዊ መንገድ ስልጣን ለማስረከብ ካልፈለጉ ግን በሃይል እስኪወገዱ ድረስ በስልጣን ይቆያሉ። በሃይል ከተሸነፉ እንደ የደርጎቹ ከሀገር ተጠርገው ይባረራሉ፤ የደርግ ባለስልጣናት ዕጣ ፈንታ ይቀምሳሉ።
ስልጣን ለህዝብ እናስረክብ፤ ሰለማዊ የስልጣን ሽግግር ይኑር። ስልጣን ለህዝብ ካላስረከብን ግን ሌላ ታጣቂ ሃይል ይነጥቀዋል። ከዛ ስልጣን ባላንጣን መምችያ ዱላ ይሆናል። ዱላው ከህዝብ ጋር መሆን አለበት።

==================
ሰላማዊ ሰልፍ በደርግና ህወሓት

“የትግራይ ህዝብ ሰለማዊ ሰልፍ የማድረግ መብቱ ከተነፈገ እነሆ 22 ዓመታት አለፉ” ብዬ ለፃፍኩት “ከ22 ዓመታት በፊት ሰለማዊ ሰልፍ ማድረግ ይፈቀድ ነበር እንዴ? በደርግ ግዜስ ሰለማዊ ሰልፍ ይፈቀድ ነበር ማለት ነው?” የሚል ጥያቄ መጣብኝ።

የደርግ ዘመን በትግራይ ክልል የጦርነት ግዜ ነበረ። በጦርነት ግዜ ሰለማዊ ሰልፍ አይፈቀድም። በደርግ ግዜ ሰለማዊ ሰልፍ ማድረግ በህገመንግስት የተደነገገ መብት አልነበረም። በደርግ ዘመን ስርዓት አልነበረም። ደርግ ትግራይን አልተቆጣጠረም ነበር። ግማሹ የትግራይ መሬት በደርግ ወታድሮች ቁጥጥር ሲሆን ግማሹ ደግሞ በህወሓቶች እጅ ነበረ (ሓራ መሬት ትግራይ)። ስለዚህ አንድ መንግስት የዜጎችን መብት ለማስከበር መጀመርያ ስርዓት መመስረት አለበት። በሁሉም አከባቢዎች አስተዳዳራዊ ስራና ቁጥጥር ሊኖረው ይገባል። ደርግ በትግራይ አስተዳዳራዊ ቁጥጥር አልነበረውም። የዜጎችን መብት ለማስከበር ሕገመንግስት መደንገግ አለበት። በደርግ ግዜ ሕገመንግስት አልተደነገገም ነበር ማለት ይቻላል። ምክንያቱም ደርግ ወታደራዊ መንግስት ነበርና። ወታደራዊ መንግስት ሕግ አያከብርም፤ ስለ ስልጣኑ እንጂ ስለ ህዝብ መብት አይጨነቅም።

ስለዚህ የትግራይ ህዝብ ሰለማዊ ሰልፍ የማድረግ መብቱ ተነፈገ ሲል በደርግ ግዜ መብቱ ተከብሮለት ነበር ማለቴ አይደለም። መልእክቱ ህወሓትም ከደርግ እሻላለሁ፣ ደርግን አስወግጄ የህዝብ መብት አስከብራለሁ፣ ነፃነት እፈቅዳለሁ እያለ የትግራይን ህዝብ ድጋፍ አሰባስቦ ቤተመንግስት ከገባ በኋላ ሌላ ደርግ ሆነብን ለማለት ተፈልጎ ነው።

ህወሓት ራሱ ከደርግ ጋር ማወዳደር ቢተው ጥሩ ይመስለኛል። ምክንያቱም በደርግ ግዜኮ (በትግራይ ማለቴ ነው) ስርዓት አልነበረም። የደርግ ዘመንኮ የጦርነት ዘመን ነው የነበረው። ስለዚህ አንድ መንግስትነት ተቆጣጥርያለሁ የሚል ስርዓት ራሱ ከጦርነት ዘመን ጋር እንዴት ያወዳድራል? ህወሓት ራሱ መፈተሽ ያለበት አሁን መስራት ካለበትና መስራት ከሚጠበቅበት አንፃር መሆን አለበት።

ፋሲል የኔዓለምን የምተችበት ምክንያት አገኘሁ! • ‹‹መሬት ተሸጠ አልተሸጠ›› ኢህአዴግ መደገፍን ምን አመጣው?

$
0
0

ከጌታቸው ሽፈራው

ጋዜጠኛ ፋሲል የኔዓለም ሰሞኑን ‹‹ኢህአዴግን የምደግፍበት አንድ ምክንያት አገኘሁ፡፡ መሬት አይሸጥም፤ አይለወጥም›› የሚል ጽሁፍ አስነብቦናል፡፡ በአሁኑ ወቅት ስርዓቱን የሚተቹ ወይንም የሚቃወሙ ኢትዮጵያውያን ‹‹ኢህአዴግን የምደግፍበት ምክንያት አገኘሁ›› ማለት ይቅርና ትችታቸው የሰላ ሆኖ ካልተገኘ ‹‹ወያኔ›› መባላቸው የተለመደ ሆኗል፡፡ ምክንያቱ ምንም ይሁን ምን ፋሲል ይህንን የፖለቲካ ባህላችን እያወቀና ደፍሮ ‹‹ኢህአዴግን የምደግፍበት አንድ ምክንያት አገኘሁ!›› ማለቱ በራሱ ይበል የሚያሰኝ አዲስ ባህል ነው፡፡
በእርግጥ ፋሲል ኢህአዴግን እደግፈዋለሁ ሲል በጭፍን አይደለም፡፡ ከግራ ፖለቲካው የተቀነጨበ ‹‹ካፒታሊስቶች መሬቱን ተቆጣጥረው አርሶ አደሩን መሬት አልባ ያደርጉታል፡፡›› የሚል መከራከሪያ አንስቷል፡፡ ይህ መከራከሪያ በዚህ ዘመን ደግሞም ፋሲል እደግፈዋለሁ ያለው ኢህአደግ ራሱም ሆነ በቅርቡ የሚገኙት ባለሃብቶች መሬትን በተቆጣጠሩበት በአሁኑ ወቅት ባይሆን ኖሮ ‹‹ለአቅመ መከራከሪያነት›› ብቁ በሆነ ነበር፡፡

‹‹መደገፍን ምን አመጣው?››

የአዲስ አበባ ከተማ ገጽታ (ፎቶ ከፋይል)

የአዲስ አበባ ከተማ ገጽታ (ፎቶ ከፋይል)

ፋሲል በአሁኑ ወቅት መሬት ቢሸጥ ቢለወጥ በተወሰኑ የስርዓቱ ደጋፊ ካፒታሊስቶች እንደሚያዝ ሲፈራ ስርዓቱ በመሬት ጉዳይም ብልሹ መሆኑን እየገለጸልን ነው፡፡ ታዲያ የዚህ ብልሹ ስርዓት ተግባራዊ የማትሆን አንዲት ዘለላ ‹‹መርሁ›› እንዴት ትደገፋለች? ኢህአዴግ መሬትን አይሸጥም አይለወጥም የሚለው አርሶ አደሩን ጨምድዶ ለመያዝ እንደሆነ ፋሲልን መምከር የሚቻል አይደለም፡፡ በዚህ መንገድ ኢህአዴግ ዘመናዊ ጭሰኛ መፍጠሩ መቼም ቢሆን ድጋፍ ሊያስገኝለት አይችልም፡፡
በሌላ መልኩ የፋሲል መደገፊያ ምክንያትም ቢሆን በአሁኑ እርስ በእርሱ የሚጋጭ ነው፡፡ ፋሲል መሬት ቢሸጥ ቢለወጥ ካፒታሊስቶች መሬት ስለሚያካብቱ የአርሶ አደሩ መሬት በጥቂት ግለሰቦች እጅ ይወድቃል ይለናል፡፡ በሌላ መልኩ ደግሞ ህወሓት/ኢህአዴግ የጥቂቶች መንግስት መሆኑን ይነግረናል፡፡ መሬት የ‹‹መንግስት ነው!›› ሲባል ህወሓት/ኢህአዴግ ባለስልጣናትን ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ጥቅምን ከማስጠበቅ ውጭ ‹‹መንግስት›› በሚባለው መዋቅር እያገለገለ ነው ሊለን አይችልም፡፡ ስለሆነም ወረቀት ላይ ‹‹መሬት አይሸጥም አይለወጥም›› ተብሎም ቢሆን መላው የአገሪቱ መሬት ጥቂቶቹ ገዥዎች እንደፈገሉ የሚጠቀሙበት ከመሆን አልዳነም፡፡
ለኢህአዴግ ምቹ እስከሆነ ድረስ የትኛውም ካፒታሊስት የቻለውን ያህል መሬት የማካበት መብት ተሰጥቶታል፡፡ እነ አላሙዲን መሬት እስከፈለጉ ድረስ የተፈናቀለው አርሶ አደር ተፈናቅሎ አርሰው የማይጨርሱት መሬት ለ99 አመት በነጻ በሚባል ዋጋ እየተሰጣቸው ነው፡፡ በእርግጥ በየ ክፍለ ሀገሩ ብቻ ሳይሆን አዲስ አበባም ውስጥ ድሃዎች ተፈናቅለው ሰፋፊ መሬቶች ምንም ሳይሰራባቸው ፋሲል ‹‹መሬቱን ይቆጣጠሩታል!›› ብሎ በሚፈራቸው ካፒታሊስቶች ያለምንም ተግባር ታጥሮ ይገኛል፡፡ ምን አልባት ይህ ነገር የተባባሰው ፋሲል ከአገር ከወጣ ከሆነ አላውቅም፡፡
በአንድ ወቅት ጋምቤላ ውስጥ የተሰራ ጥናት የክልሉን ሰፋፊ መሬት የተቆጣጠሩት 75 በመቶ የሚሆኑት የህወሓት ሰዎች መሆናቸውን ይፋ ማድረጉ ይታወቃል፡፡ ይህን ጉዳይ ኢሳትም ሰፊ ዘገባ ሰጥቶት እንደነበር ይታወቃልና ለእነ ፋሲል አዲስ ሊሆን አይችልም፡፡ ስለ ሰብዓዊ መብት፣ ዴሞክራሲና ሌሎች ጉዳዮች የማያነሱ ካፒታሊስቶች መሬት ከጠየቁ የፈለጉት ቦታ ላይ ይሰጣቸዋል፡፡ አላሙዲን ሳውዲዎችን ይዞ ኢትዮጵያ ውስጥ ገብቷል፡፡ የቱርክ፣ የህንድ፣ የኳታር…… ካፒታሊስቶች ኢትዮጵያውያንን እምብዛም ለማይጠቅም አበባ፣ ሩዝና ሌሎቹንም ምርቶች ለማምረት አርሶ አደሮችን እያፈናቀሉ ቀጥለዋል፡፡ አርሶ አደሩ እየተፈናቀለ ለ99 አመት በሲጋራ ዋጋ እየተሸጠላቸው ነው፡፡ ታዲያ መሬት በይፋ ‹‹ይሸጥ›› ቢባልስ ከዚህ በላይ ምን ያህል አርሶ አደር እንዳልተፈናቀለ ነው? ከዚህ የባሰ ምን ያህል ወረራስ እንዳልተደረገብን ነበር?

ከምንም በላይ ፋሲል ‹‹መሬት አይሸጥም አይለወጥም!›› የሚለውን የኢህአዴግን አቋም ለኢትዮጵያ አስቦ ያስቀመጠው ያህል አስቦት ‹‹እደግፈዋለሁ!›› ማለቱ ነው የሚገርመው፡፡ ኢህአዴግ ወረቀት ላይ ‹‹መሬት አይሸጥም አይለወጥም!›› ማለቱን እንደ እውነት ቆጥሮም አንድ መደገፊያ ነጥብ ማስቀመጡ ግራ የሚያጋባ ነው፡፡ ህወሓት/ኢህአዴግ አርሶ አደሩን የስልጣን ምንጭ አድርጎ ስለሚመለከት መሬትን በመያዢያነት መጠቀሙ ለማንም ግልጽ ነው፡፡ መሬትን በይፋ መሸጡ ኢህአዴግን ተጨማሪ አንድ ቀን የሚያቆየው መስሎ ከታየው ዛሬውኑ እንደሚሸጠው ጥርጥር የለውም፡፡ ኢህአዴግ ፋሲል ከሚፈራው ‹‹ካፒታሊስቶች››ና ከአርሶ አደሩ የትኛው እንደሚጠቅመው ያውቃል፡፡ በእርግጥ ሁለቱንም አብሮ ማስኬድ ችሏል፡፡ ፋሲል መሬት ‹‹ካልተሸጠ›› መሬት አያክብቱም ያላቸው ካፒታሊስቶች ‹‹እድሜ ለኢህአዴን!›› እንጅ አርሰው የማይጨርሱት መሬት ከአርሶ አደሩ ነጥቀው አጥረዋል፡፡ ቀሪውን የአርሶ አደሩን መሬት ደግሞ ‹‹አይሸጥም አይለወጥም!›› ብሎ የሚገዛና ምቹ ካፒታሊስት እስኪመጣ ድረስ ጨምድዶ ይዞታል፡፡ በሁለቱ መካከል ግን ፋሲል የሚለው ኢህአዴግና ‹‹መርሁ›› የለም፡፡ አንደኛ ነገር እሱ ለእራሱ እስጠቀመ ድረስ እንጅ ለአገር ብሎ አይደለም‹‹አልሸጥም!›› የሚለው፡፡ ደግሞም ፋሲል ለፈራቸው ካፒታሊስቶች እንደፈለጉ እየቸበቸበላቸው ነው፡፡
እንዲያው ለካፒታሊስቱ ባይሸጥ ኖሮስ ከነ ሌሎቹ ድክመቶቹ መሬትን አልሸጠም ተብሎ እንዴት ይደገፋል? በኢትዮጵያ ፖለቲካ መሬት ብቸኛው የልዩነት መስመር አይደለም፡፡ መሬት ከሚዲያ ነጻነት፣ ከዴሞክራሲያዊና ነጻ ምርጫ፣ ከፍትህ…..ብቻ ከበርካታ ጥያቄዎች መካከል አንዱ እንጅ ብቸኛው ሆኖ አያውቅም፡፡

አንድ ምሳሌ ላንሳ!

ኢህአዴግ ኢትዮጵያውያንን ያስራል፣ ያፈናቅላል፣ ከመብቶቻቸው ይገድባል፡፡ ለአብነት ያህል እነ እስክንድር ጠያቂ ከልክሏቸዋል፡፡ እስር ቤት ውስጥ ችግር ይደርስባቸዋል፡፡ የታሳሪዎች ቤተሰቦች ይጉላላሉ፡፡ በህገ ወጥ መንገድ ከመታሰራቸውም በላይ እስር ቤት ውስጥ በርካታ ችግሮች ይገጥማቸዋል፡፡ ኢህአዴግ የእነ እስክንድር የፍርድ ጉዳይ ባለው ህገ ወጥነት እንደቀጠለ ከበርካታ ችግሮቻቸውና ጥያቄዎቻቸው መካከል አንዱን ቢፈቅድ ልንደግፍው ነው ማለት ነው፡፡ እኔ የፋሲልን መርህ ከዚህ በተመሳሳይ ነው የማየው፡፡ ምን አልባት የመሬት ጥያቄ ቢመለስ እንኳ በኢህአዴግ ላይ የምናደርገውን መማረር (ተቃውሞ) ወደ ሌሎቹ ጉዳዮች ይቀይረዋል አሊያም ምሬታችን ይቀንሰዋል እንጅ ሊደገፍ አይገባውም፡፡ የሚገባህን የቀማህን አካል ጮኸህም ሆነ እንዲሁ ሲመልስልህ በዛ ቅጽበት ‹‹አንድ፣ ሁለት፣ ሶስት፣….›› እያልክ ‹‹በምክንያት›› ልትደግፈው አትችልም፡፡ ምክንያቱም ያችን አንዲት ነገር መልሶም (ፋሲል ላልተመለሰው ነው የደገፈው) ጥፋተኛ ስለሆነ ማማረርክን፣ መቃወምክን ልታቆም አትችልም፡፡ ኢህአዴግ በመሬት ጉዳይ ከብልሹነት አልወጣም፡፡
በዚህ ብልሹ ዘመን መሬት በግልጽ ቢከፋፈል ጉዳት ያመጣ ነበር ተብሎ ‹‹በምክንያት›› መደገፍ መንግስት ያለ ህግ መነሻ አስሮ ጠያቂ ለከለከለው እስረኛ ጠያቂ ሲፈቅድ ‹‹አንድ ምክንያት›› ጠቅሶ እንደመደገፍ ነው፡፡ አሊያም ሁለት ሶስት እቃ መስረቅ ይችል ነበር ተብሎ የተገመተን ሌባ አንድ እቃ ሰርቆ ስለወጣ ይህን ሌባ የመመረቅ ያህል ነው፡፡ ሌባ ሌብነቱን፣ ብልሹ መንግስት ብልሹነቱን ጨርሶ እስካላቆመ ድረስ ከብልሹነቶቹ መካከል ሳይመቼው ስለቀረ አሊያም ስላላሰበው ብቻ አንዱን ወይንም ሁለቱን ስለተወ አሊያም ስላልፈጸመ ሊያስደግፈው የሚገባ አይመስለኝም፡፡ በመርህ የምናምን ከሆነ ማለቴ ነው!

በሐዋሳ ከተማ 2 ትምህርት ቤቶች በቋንቋ የተነሳ ብጥብጥ ተነስቶ ሰዎች ቆሰሉ

$
0
0

hawasa federal policeከዳዊት ሰለሞን

በሀዋሳ ከተማ ታቦር 2ኛ ደረጃ ት/ቤት የሚማሩ የሲዳማ ተወላጆች የሚኒ ሚዲያ ፕሮግራም በሲዳመኛ ቋንቋ ይተላለፍ፣ ታቦር 2ኛ ደረጃ ት/ቤት የሚለውን ታፔላ በሲዳመኛ ቋንቋ ይጻፍ በሚል መነሻና ከቋንቋ ጋር በተያያዘ ከፍተኛ ረብሻ ተፈጥሮ የፌደራል ፖሊሶች ወደ ግቢው ሲጠጉ ተማሪዎቹ ድንጋይ በመወርወር በርካታ ፖሊሶች ቆስለዋል፡፡ ፖሊሶቹ በወሰዱት ርምጃ ብዙዎች ለጉዳት ተዳርገዋል፡፡

በሐዋሳ ከተማ በሚገኙ ሁለት የከፍተኛ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ውስጥ የሚገኙ ተማሪዎች እንደቀሰቀሱት በተገመተ ረብሻ ከፍተኛ ጉዳት በተማሪዎችና በአስተማሪዎች ላይ መድረሱ ተሰምቷል፡፡

የትምህርት ቤቱ የመማሪያ ቋንቋ እንዲለወጥ በጠየቁ የኦሮሞ ተወላጆችና በሲዳማ ተወላጆች መካከል ረብሻው መቀስቀሱን ከስፍራው ያናገርኳቸው ሰዎች በስልክ ገልጸውልኛል፡፡ ረብሻውን ለማብረድ ፖሊሶች መሳሪያ መተኮስ በመጀመራቸውም የተጎዱ ሰዎች ሊኖሩ እንደሚችሉ ተገምቷል፡፡ ይህ ዜና እስከተጠናቀረበት ሰዓት ድረስ ሐዋሳ ውስጥ የተኩስ ድምጽ ያለ ማቋረጥ እንደሚሰማም ምንጮች ተናግረዋል።

እግረ ሙቅ/እግር ብረት/ ዮሴፍ ሽፈራው(ጀርመን)

$
0
0

ዮሴፍ ሽፈራው(ጀርመን)

ከንጉሱ ዘመን ጀምሮ ዘውዳዊውን አገዛዝ በመቃወም የለውጥ መርህን አንግበው የተነሱትን የተማሪውን እና የሰራተኛውን ክፍል ወገኖች እንቅስቃሴ ለማኮላሸት እስር እንግልት እና ግድያ ሲፈፀም ቆይቷል።

በወቅቱ እንደ ከርቸሌ በመሳሰሉት እስር ቤቶች የታጎሩት ወገኖች በጠባብ ክፍል ከመወሰናቸውም በተጨማሪ በእግረ ሙቅ/እግር ብረት/ ታሰረው እንዲሰቃዩ ይደረግ ነበር።

PBw

ንጉሱን በሀይል በማሶገድ ወደ ስልጣን የመጣው ወታደራዊው ደርግ በስልጣን ዘመኑ የመብት ጥያቄ ያነሱትን ብርቅዬ የኢትዮጵያ ልጆች በጅምላ እያፈሰ ከማሰሩም በላይ የብዙዎቹን ህይወት ቀጥፋል።በዚህም አንድ ትውልድ ያጠፋ መንግስት በመባል ይታወቃል።

ደርግ እንደ ከርቸሌ ማዕከላዊ እና ደርግ ጽ/ቤት በመሳሰሉት እስር ቤቶች ባሰራቸው የፖለቲካ እስረኞች ላይ ለማመን የሚቸግር ዘግናኝ ድርጊት ሲፈጽምባቸው ቆይቷል።ስፍር ቁጥር የሌላቸውን ዜጐች በፖለቲካ አቋማቸው ብቻ በጊዜው በነበሩት ባለስልጣናት ይፈፅምባቸው ከነበረው ሰብዓዊ መብት ጥሰት ብዛት የተነሳ እዛው እስርቤት እያሉ ህይወታቸው ያልፋል።

ከ22 ዓመታት በፊት ወታደራዊውን ደርግ በመጣል ስልጣን የተቆናጠጠው ወያኔ/ኢህአዴግ/ የዜጐቹን የመብት ጥያቄ ከመመለስ ይልቅ ከቀደሙት የአገሪቷ መሪዎች በባሰ መልኩ እጅግ ከፍተኛ የፖለቲካ እስረኛ በአገሪቱ እንዲኖር አድርጓዋል።

በአቶ አሊ ሁሴን የሚመራው የኢትዮጵያ የፖለቲካ እስረኞች አንድነት ኮሚቴ /Solidarity Committee For Ethiopian Political Prisoners/  እንደዘገበው በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ በተለያዩ እስር ቤቶች ከ 37,000 በላይ የፖለቲካ እስረኞች ይገኛሉ።

ወያኔ/ኢህአዴግ/ እንደ ቅሊንጦ የመሳሰሉ በርካታ አዳዲስ እስር ቤቶች ለአፈና አላማው ሲል አስገንብቷል። ቀድሞ በነበሩት እንደ ቃሊቲና ዝዋይ ማረሚያ ቤቶች ውስጥ ደግሞ በአንድ ክፍል በርካታ እስረኞች በተጨናነቀ ሁኔታ እንዲኖሩ በማድረግ ጨካኝነቱን በተግባር እያሳየ ነው።

የኢሳቱ ጋዜጠኞ ሲሳይ አጌና የእስር ዘመኑን ባስታወሰበት  ”የቃሊቲው መንግስት” በሚለው መፅሐፉ ምርጫ 97ን ተከትሎ የተነሳውን ህዝባዊ ዓመፅ በሀይል ያፈነው ወያኔ/ኢህአዴግ/ በቃሊቲ በአንድ አዳራሽ 250 እስረኞች እደሚታሰሩ አጋልጧል። ከነዚህም መካከል 6 የሚሆኑት የአህምሮ ህሙማን ነበሩ።ሁሉም እስረኞች ለበሽታና ለሞት ተጋላጭ እዲሆኑ ለማድረግ ሲባል ከ 50 ያላነሱት የሳነባ ነቀርሳ ተጠቂዎች አብረው ታስረዋል።

በአገሪቷ ያሉትን ማረሚያ ቤቶች የሚያሰተዳድሩት የፌደራል ፖሊስ አባላት ለገዥው ፓርቲ የወገኑ ከመሆናቸው በተጨማሪ በእስር ቤቶች ውስጥ በተገነቡ ድብቅ ማሰቃያ ቤቶች የፖለቲካ እስረኞችን በከፋ ሁኔታ ያሰቃያሉ።

የኢትዮጵያ  ህገመንግስት አንቀጽ 19 ቁጥር 3 የተያዙ ሰዎችን በተመለከተ “የተያዙ ሰዎች በአርባ ስምንት ሰዓታት ውስጥ ፍርድ ቤት መቅረብ አለባቸው”/Everyone shall have the right to be brought before a court of law within 48 hours after his arrest./  ይላል። ገዥው ፓርቲ ለዚህ ድንጋጌ ምንም ክብር የለውም።

በመሆኑም ምንም አይነት ክስ ሳይመሰረትባቸው ሁለት ዓመት እና ከዛ በላይ በእስር የቆዩ  በርካታ የፖለቲካ እስረኞች በአገሪቷ ባሉ እስር ቤቶች በብዛት ይገኛሉ።

ወያኔ/ኢህአዴግ/ የአገሪቷን ህገመንግስት ከማስከበር ይልቅ የተለያዩ ሀሰተኛ ክሶችን ለመመስረት የጠቀምበታል። ይህ ደግሞ ፍትሃዊ የሆነ የፖለቲካ እስረኞች አያያዝ እና ፍትሐዊ የፍርድ ሂደት በአገሪቷ እንዳይኖር ትልቅ እንቅፋት ሆኗል።

ዜጐች ህገመንግስቱ ያጎናጽፋቸውን የመናገር፣የመጻፉ፣የመሰብሰብ፣የመደራጀት፣ነፃ ሚዲያ፤ነፃ ምርጫ ቦድ፣ነፃ እና ገለልተኛ ፖሊስ፣ ነፃ እና ገለልተኛ መከላከያ ሰራዊት፣ፍትሃዊ ፍርድ ሂደት፣ የፈለጉትን ፓርቲ መደገፍ ፣መምረጥ፣መመረጥ፣የመማር፣የመስራት፣በአገራቸው ሀብት ማፍራት፣ከቦታ ቦታ መንቀሳቀስ፣ የሀይማኖት ነፃነት መከበር ይህንን እና መሰል ጥያቄዎችን አንግበው ከመቼውም በላይ ትግላቸውን አጠናክረው ቀጥለዋል።

ይህ ትግል የወለዳቸው እንደ አንዱዓለም አራጌ፣በቀለ ገርባ፣ርዕዮት አለሙ፣የሱፍ ጌታቸው፣እስክንድር ነጋ፣ናትናኤል መኮንን፣ኦልባና ሌሊሳ፣አቡበከር አህመድ፣ውብሸት ታየና ሌሎች በብዙ ሺ የሚቆጠሩ ዜጐች ዛሬም ድረስ በእስር ላይ ይገኛሉ።

በአሁኑ ወቅት ወያኔ/ኢህአዴግ/ የፖለቲካ እንቅስቃሴ የሚያደርጉትን ብቻ ሳይሆን እያንዳንዱን ዜጋ በፍራቻ የሚያይና የሚያሳድድ ሆኗል። በዚህ ምክንያት ተማሪው፣ አሰተማሪው፣ነጋዴው፣ሰራተኛው ፣ገበሬው፣የሀይማኖት መሪውና ስራ አጡ እየተዋከበ ነው።አንድ ላምስት በሚል የአፈና መዋቅር /እግረ ሙቅ/ ታፍኖ ተይዞል።

አገሪቷም ከአገርነት ወደ ትልቅ እስር ቤት ተቀይራለች። የወያኔ የፖለቲካ ደባ ድንበር ተሻግሮ በሽርክና በሚሰራባቸው አገሮች እየታየ ነው።ከዚህ ጋር በተያያዘ ኢትዮጵያን ዜጐች በፖለቲካ አቋማቸው ምክንያት ከሀገር ተሰደው በሚኖሩባቸው በኬንያ፣በሱዳን፣በግብጽ፣ደቡብ አፍሪካ፣በቱርክ፣እንዲሁም በሌሎች አገሮች እስር ቤቶች ውስጥ ይገኛሉ።

የወያኔ ግፍ ማቆሚያ የለውም።ማቆሚያ የሚኖረው ይህ አንባገነን መንግስት ተወግዶ ሁሉም ኢትዮጵያዊ ከታሰረበት እግረ ሙቅ/እግር ብረት/ ሲላቀቅ ብቻ ነው።ስለዚህ ሁላችንም የጋራ ክንዳችንን በማንሳት የተከበረች ሉአላዊት ኢትዮጵያ ዳግም እውን እንድትሆን የበኩላችንን አስተዋፆ እናድርግ።

ድል ለህሊና እስረኞች!!!

 

 

 

 

 


የኦሮሞ ሊቃውንት በጎጃም (ዓሰገድ ጣመነ)

$
0
0

ዓሰገድ ጣመነ

ከጎጃም ታላላቅ ሊቃውንት ውስጥ የኦሮሞ ተወላጅ የሆኑት ሁነኛ ደረጃ ይዘው ይገኛሉ፡፡ የኦሮሞ ሊቃውንት በየትኛውም የጎጃም አድባራትና ገዳማት ለትውልድ የሚተላለፉ ታላላቅ ሥራዎችን ሠርተው አልፈዋል፡፡ በአሁኑ ሰዓትም በየገዳማቱና አድባራቱ በመምህርነት የሚያገለግሉ የኦሮሞ ሊቃውንት በጎጃም ሞልተዋል፡፡
ታዋቂ ከሆኑት ሊቃውንት ውስጥ አለቃ ተክለ ኢየሱስ ዋቅጅራ፣ ታላቁ ሊቅ መምህር ገብረ ሥላሴ ክንፉ ዘደብረ ኤልያስ፣ ታላቁ ምሁር መልአከ ብርሃን ፋንታ ገብርየ (በጥናት የሚረጋገጥ) ታዋቂው የቅኔ መምህር ሀብተ ኢየሱስ ጋረደው ዘመርጡ ለማርያም (በአሁኑ ጊዜ በሕይወት የሚገኙ)፣ መምህር ወልደ ሚካኤል (በአሁኑ ጊዜ የደብረ ገነት ኤልያስ የአቋቋም መምህር)፣ መሪጌታ ወልዴ ዘሆሮጉድሩ የጫቢ ማርያም የቅኔ መምህር እና ሌሎች ተጠቃሾች ናቸው፡፡
EthiopianProvincesከጥንት ዘመን ጀምሮ በአለው ሃይማኖታዊ ሥርዓተ ትምህርት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ያለምንም አድልዎ የብሔረሰቦቿንና የዜጎችን እኩልነት አክብራ ለክብር፣ ለወግ ለማዕረግ ስታበቃ መኖርዋ በምሳሌነት እንድትጠቀስ ያደርጋታል፡፡ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ትምህርትዋን ይትበሀሏን፣ ታሪኳን፣ ቀኖናዋን (አስተምህሮዋን) ዘር፣ ቀለም፣ ቋንቋ ሳትለይ በፍቅር፣ በእናትነት አምሳል እውቀትን፣ እውነትን ለልጆችዋ መግባ፣ ተንከባክባ ስታሳድግና ለከፍተኛ ኃላፊነት ስታበቃ ኖራለች፡፡ የቤተ ክርስቲያኒቱ ልጆች ድንበር ሳያግዳቸው፣ ወንዝ ሳይገድባቸው፣ ከምሥራቅ እስከ ምዕራብ፣ ከሰሜን እስከ ደቡብ እየተዘዋወሩ ሲማሩ ኖረዋል፡፡ ትምህርታቸውን ሲጨርሱም ቢፈልጉ ወደ ቀያቸው ይመለሳሉ፡፡ ባይፈልጉ በፈለጉበት ቦታ ወንበር ዘርግተው፣ ጉባኤ አስፋፍተው በማስተማር ተከብረው ተፈርተው ይኖራሉ፡፡
በዚህ ረገድ ቤተክርስቲያኒቱ ነቀፌታ፣ ስሐ፣ እንከን የለባትም፡፡ ትክክለኛ ፍትሕና ርትዕን መሠረት አድርጋ አብሮ የመኖርን፣ የመተባበርንን፣ የመተዛዘን፣ የርኅራኄን፣ የልግስናን መርሕ ስለምታስተምር የዘር፣ የጎሣ፣ የቀለም፣ የብሔር ጣጣ የለባትም፡፡ (ትምህርትን በማዳረስ ረገድ ማለቴ ነው) የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ከምንም በላይና ከማንም በፊት ነጻነትንና ዲሞክራሲን ያስከበረች የእውቀት ማዕከል መሆንዋን ማንም ሊክደው አይችልም፡፡ ይህ አገላለጽ በአሁኑ ሰዓት በማዕረግ፣ በሥልጣን የሚናከሱትንና በሙስና የተዘፈቁትን የቤተክህነት አንዳንድ ባለሥልጣኖችንና አስተዳዳሪዎችን አይመለከትም፡፡
ለዚህ ጽሑፌ መነሻ የሆነኝ የካቲት 22 እና 23 ቀን 2006 ዓ.ም የደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ የሐዲስ ዓለማየሁ የባህል ጥናት ተቋም ሁለተኛ ዓመታዊ ዐውደ ጥናቱን በአካሔደበት ወቅት የሐምቡርግ ዩኒቨርሲቲ (ጀርመን) መምህር የሆኑት ዶ/ር ጌቴ ገላየ ስለአለቃ ተክለ ኢየሱስ ዋቅጅራ ሥራዎች ያቀረቡት ጥናታዊ ጽሑፍ ነው፡፡ አለቃ ተክለ ኢየሱስ ዋቅጅራ የንጉሥ ተክለ ሃይማኖትንና የጎጃምን ታሪክ መሠረት አድርገው በጻፉት መጽሐፍና በኋላም ሥርግው ገላው (ዶ/ር) “የኢትዮጵያ ታሪክ በአለቃ ተክለ ኢየሱስ” በሚል በ2002 ዓ.ም በአሳተሙት መጽሐፍ ውስጥ የሚገኙትንና ታሪካዊነት ያላቸውን በርካታ የአማርኛ ግጥሞችን ከወቅትና ከታሪክ ኹኔታ ጋር እያዛመዱ፣ ዶ/ር ጌቴ ገላየ በዐውደ ጥናቱ ላይ በትንታኔ መልክ አቅርበዋቸው ነበር፡፡
በታሪክ ሰነድነት ስለሚጠቅሙት ስለ ታሪካዊ ግጥሞቹ ይዘት ወደፊት ቅኝት የሚደረግ ሲሆን አሁን አለቃ ተክሌን ጨምሮ ከላይ ስለጠቀስኳቸውና በጎጃም ስለሚታወቁት የኦሮሞ ሊቃውንት ማንነት ለማስተዋወቅ እሞክራለሁ፡፡
በመጀመሪያ ትኩረቴ በታዋቂው ሠዓሊና የታሪክ ጸሐፊ በሆኑት አለቃ ተክለ ኢየሱስ ዋቅጅራ ላይ ይሆናል፡፡ አለቃ ተክለ ኢየሱስ ከመጀመሪያ መጽሐፋቸው ሌላ በግርማ ጌታሁን አዘጋጅነት “የጎጃም ትውልድ በሙሉ ከአባይ እስከ አባይ” የሚለው መጽሐፋቸው በ2003 ዓ.ም ታትሞላቸዋል፡፡”
ስለ አለቃ ተክለ ኢየሱስ ዋቅጅራ ሥራዎች በደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ በዶ/ር ጌቴ በቀረቡበትና ውይይት በተካሄደበት ወቅት አንድ ተሰብሳቢ /እኔው እራሴ/ በርካታ የኦሮሞ ሊቃውንት በጎጃም መኖራቸውን በስም ገልጬ፣ “እንደነዚህ ዓይነት ታላላቅ ሥራዎችን እንዲሠሩልን አሁንም ሰዎች ሁሉ ምነው ከወለጋና ከሌሎች የኦሮሚያ ክልሎች በመጡልን” ስል ተሰብሳቢዎች በከፍተኛ ስሜት አጨበጨቡ፡፡
ይህ የጭብጨባ ስሜት አብሮ የመኖርን፤ በባህል፣ በቋንቋ በታሪክ መተሳሰርን፤ ፍቅርን፣ መከባበርን፣ አንድነትን የሚገልጽ ታላቅ የስሜት ወላፈን ነው፡፡ ከዚህ ስሜት በመነሣት በአሁኑ ጊዜ የኢትዮጵያ ደራስያን ማኅበር ፕሬዚዳንት የሆኑት ዶ/ር ሙሴ ያዕቆብ በእንደዚህ ዓይነቱ ዐውደ ጥናት ላይ ከወለጋና ከሌሎች በኦሮሚያ ከሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች ጭምር ምሁራንና ሌሎች ተሳታፊዎች እንዲጠሩ ቢደረግ መልካም እንደሆነ አሳስበው፣ በዚህ የሕዝቦች መስተጋብር ዙሪያ በሰፊው ሥራ መሠራት እንዳለበት አጽንዖት ሰጥተውበታል፡፡
ዶ/ር ሥርግው ገላው በመጽሐፋቸው መግቢያ ላይ እንደሚጠቅሱትና አድማሱ ጀምበሬም በመጽሐፈ ቅኔያቸው 1963 ላይ እንዳሰፈሩት፤ አለቃ ተክለ ኢየሱስ የመጀመሪያ ስማቸው ነገሮ ነው፤ አባታቸው ዋቅጅራ፣ እናታቸው ገላኔ ይባላሉ። ተክለ ኢየሱስ በ1871 ዓ.ም የ7 ዓመት ልጅ ነበርኩ ብለው ስለጻፉ በ1864 ዓ.ም አካባቢ ኩታይ ውስጥ እንደተወለዱ ይገመታል፡፡
በዶ/ር ሥርግው ገላው ሐተታ መሠረት፤ ራስ አዳል ተሰማ (በኋላ ንጉሥ ተክለ ሃይማኖት) ወደ ኩታይ የዛሬዋ ምሥራቅ ወለጋ ዘምተው አቡናንና አዋጠን ባቀኑበት ወቅት አጎታቸው የሌምቱ ጎሹ የዘመቻቸው ተካፋይ ነበሩ፡፡ በዚህ ወቅት የሌምቱ ጎሹ 8 ሕፃናትን ከኩታይ ይዘው ወደ ሀገራቸው ደብረ ድሙና (ጎጃም) ተመለሱ፡፡ ሕፃናቱም አጋ፣ ደንገላ፣ ፈይሳ፣ ዋቅጅራ፣ ወቅኬኒ፣ ጅራታ፣ አገሾ፣ ነገሮ ይባላሉ፡፡ ከተጠቀሱት ሕፃናት ውስጥ ነገሮ በኋላ ተክለ ኢየሱስ የተባሉት የዚህ ታሪክ ጸሐፊ ናቸው፡፡
የአለቃ ተክለ ኢየሱስ ታሪክም ልክ የታላቁ አሌክሳንደር ፑሽኪን ቅድመ አያት አብርሃም ሀኒባል በሩሲያ ንጉሠ ነገሥት፤ በቀዳማዊ ጴጥሮስ ቤተ መንግሥት ሞገስ አግኝቶ እንደነበረ ሁሉ አለቃ ተክሌም በንጉሥ ተክለ ሃይማኖት ዘንድ ከፍተኛ አክብሮት እንደነበራቸው ወደፊት እንመለከታለን። የንጉሥ ተክለሃይማኖት አስተሳሰቡም በእውቀት እንጂ በዘረኝነት ላይ የተመሠረተ እንዳልሆነ ማጤን ይገባል፡፡
ሕፃናቱ እንደየዕድላቸው በተለያየ ሙያ ሲሰማሩ፣ ነገሮ በመጀመሪያ የወንድ እልፍኝ ገበታ አቃፊ ሆኑ፡፡
አማርኛ ሲለምዱ ክርስትና ተነሥተው ዲማ አባ ሣህሉ ከተባሉ መምህር ዘንድ ገብተው የቤተክህነት ትምህርት ተማሩ፡፡ በብልህነታቸውና በአስተዋይነታቸው አሳዳጊያቸው የሊምቱ ጎሹ በእጅጉ ይደነቁ ነበርና የመሞቻ ጊዜያቸው ሲደርስ፣ ለባለቤታቸው ለወይዘሮ ስኂን ተክለ ኢየሱስንና ወልደሰንበትን አደራ ሰጥቼሻለሁና እንደልጆቻችን አርገሽ አሳድጊልኝ ብለዋቸዋል፡፡ ባለቤታቸውም አደራቸውን ተወጥተዋል፡፡
ቀድሞ ጅራታ ይባሉ የነበሩት ወልደ ሰንበት፤ ደብረ ጽሙና ተምረው የቤተ ክርስቲያን አገልጋይ ካህን (ቄስ) ሆነዋል፡፡ ተክለ ኢየሱስ ዋቅጅራ እንዲሁ ቅኔን ጨምሮ የቤተ ክህነቱን ትምህርት በሚገባ ተምረው የታወቁ ሠዓሊና ታሪክ ጸሐፊ ሆነዋል፡፡ በዲቁና ማዕረግም የገናዚ ማርያምን አገልግለዋል፡፡
በ1881 ዓ.ም ንጉሥ ተክለ ሃይማኖት ከንጉሥ ምኒልክ ጋር ለመገናኘት ወደ ቤጌምድር ሲሔዱ፣ ተክለ ኢየሱስ ዋቅጅራም ለምኒልክ የሥዕል በረከት ይዘው ከተክለ ሃይማኖት ሠራዊት ጋር ወደ ቋና ተጉዘዋል፡፡ ቋና ላይ አየለ ወሰን በተባሉ የንጉሥ ተክለ ሃይማኖት የእልፍኝ አሽከር አነሳሽነት ለንጉሥ ምኒልክ የተሣለውን የሥዕል ገጸ በረከት አለቃ ተክለ ኢየሱስ ለንጉሥ ተክለሃይማኖት አበረከቱ፡፡ ንጉሥ ተክለ ሃይማኖትም በረከቱን ተቀብለው ደመወዝ ቆረጡላቸው፡፡ ከዚያን ጊዜ ጀምሮም የተክለ ኢየሱስ ዋቅጅራ መደበኛ ሥራቸው ሥዕል ሆነ፡፡ የተዋጣላቸው ሠዓሊ እንደነበሩም ይነገርላቸዋል፡፡
አለቃ ተክለ ኢየሱስ ዋቅጅራ በሥዕል ሙያቸው የዲማ ጊዮርጊስን፣ የደብረ ማርቆስን፣ የደብረ ዘይትን፣ ማርያምን፣ የጠያሜን፣ የጣማዊትን፣ የድልማ አማኑኤልን አብያተክርስቲያናት አስጊጠዋቸዋል፡፡ የደብረ ማርቆስን መጽሐፈ ወንጌል፣ የንጉሥ ተክለ ሃይማኖትን ቤተ መንግሥትና የራስ ኃይሉን መኖሪያ ቤት በሥዕል አሸብርቀዋቸዋል፡፡
የሥዕል ትሩፋቶቻቸው በአሁኑ ሰዓት ሕያው ምሥክር ሆነው በየቤተክርስቲያኖቹ ውስጥ ይታያሉ፡፡ እኒህ ሊቅ በዘመኑ ደረጃቸውም በጎጃም ከተከበሩ ሰዎች ተርታ ስለነበር ማኅበራዊ ከበሬታ ነበራቸው፡፡ የቤተ መንግሥት መጠጫቸው በንጉሥ ተክለሃይማኖት የተበረከተ ሲሆን “ዝ ኮልባ ዘአለቃ ተክሌ ዘወሀቦ ንጉሥ ተክለሃይማኖት” ይላል፡፡ ትርጉሙም “ይህን የወይን ጠጅ መጠጫ ለተክለ ኢየሱስ የሰጠው ንጉሥ ተክለሃይማኖት ነው” የሚል ነው፡፡
ለእኒህ ጥበበኛ ሰው በጊዜው በነበረው የመተዳደሪያ ስሌት መሠረት በወር ከሚከፈላቸው አምስት ማድጋ እህልና አምስት ጠገራ ብር ሌላ በየወሩ ከሚያስተዳድሩዋት ከጥድ ማርያምና ከማቻከል የአጤ ቆሎ እህል እየተሰፈረ ይገባላቸው ነበር፡፡ እንዲሁም ከግራ ቅዳምንና ከአጫሙስ ገበያ በወር በወር በገፈፋ ቀረጥ ይገባላቸው ነበር፡፡
በንጉሡ ፈቃድ የንጉሡን ልጅ የራስ በዛብህ ሚስት የነበረችውን የወ/ሮ ተዋበች ታውቄን ልጅ ዓለሚቱ መርሻን እንዲያገቡ መደረጉ በደ/ማርቆስ ቤተ መንግሥት የነበራቸውን ማኅበራዊ ከበሬታ ያመለክታል፡፡ አለቃ ተክለ ኢየሱስ ወ/ሮ ዓለሚቱ መርሻን ሲያገቡ ንጉሡ አምስት ቁም ከብትና ሦስት አገልጋዮችን ጨምረው ሸልመዋቸዋል፡፡
በአጠቃላይ በንጉሥ ተክለ ሃይማኖት ዘመን፣ አለቃ ተክለ ኢየሱስ ዋቅጅራ በደስታ ቢኖሩም ንጉሡ ከሞቱ በኋላ ግን አስቸጋሪ ሕይወት መርተዋል፡፡ ይኸውም በራስ ኃይሉ ተንኮል (በጊዜው ደጃች ሥዩም ይባሉ ነበር) ፈቃድ የሌለው ማኅተም እንዲቀርፁ ስለተደረገ በዚህ ተወንጅለው ደጃች ስዩምም ከሥልጣናቸው ተሽረው ወደ አፍቀራ (ሸዋ) ሲጋዙ፣ አለቃ ተክለ ኢየሱስም በዓፄ ምኒልክ ትእዛዝ ወደ አዲስ አበባ መጥተው ወኅኒ ወረዱ፡፡
በመጨረሻ በእጨጌ ወልደ ጊዮርጊስ አሳሳቢነትና በእቴጌ ጣይቱ አማላጅነት ብዙ ሳይታሰሩ ተፈትተዋል፡፡ እቴጌይቱም የሥዕል ችሎታቸውን በመገንዘባቸው ጉራምባ ማርያምን እንዲስሉላቸው በየቀኑ ድግስ እንዲደገስላቸው ከማድረጋቸውም ባሻገር፣ ሦስት ዳውላ እህል ሁለት ቁንዶ በርበሬ፣ ማር፣ አንድ ሙክት፣ ለአሥር ቀን አምስት ኩባያ አሻቦና አንድ ዕቃ ቅቤ በየወሩ ደመወዝ ቆርጠውላቸው ነበር፡፡ ይህ ሁሉ ሆኖ ሸዋን ብዙም አልወደዱትም፡፡ የአዛዥ አማኑኤልን ተንኮል ለመቋቋም አቃታቸው፡፡ በዚህ ላይ ዓይናቸውን ታምመው ለመዳን ተቸገሩ፡፡ ዓይናቸውን በማስታመም ላይ እያሉ ደግሞ ሌላ ችግር ተፈጠረባቸው፡፡ በንጉሥ ተክለ ሃይማኖት ቀጣሪነት ያገቧቸው ሚስታቸው ወ/ሮ ዓለሚቱ መርሻ
“አንተም እንዳትመጣ እስርኛ ነህ ባሌ፣
እኔም እንዳልመጣ ሸዋ አይደለም ክፍሌ፣
ቶሎ ፍታኝና ፈጽሞ ልቅርብህ፣
የከብቴንም ድርሻ እንድትሰጠኝ ከፍለህ”
የሚል ደብዳቤ ኩላቸው፡፡ ከዓይናቸው ሕመም ይልቅ አለቃ ተክሌን ይኸ በጣም አሠቃያቸው፡፡ ዓፄ ምኒልክን አስፈቅደው ወደ ጎጃም ተመለሱ፡፡ ዐባይን ተሻግረው ኅዳር 30 ቀን 1895 ዓ.ም ደብረ ማርቆስ ቢደርሱም ባለቤታቸውን ወ/ሮ ዓለሚቱ መርሻን አላገኙዋቸውም፡፡ ይኸውም ከፍርሐት የተነሣ ዳሞት ከራስ መንገሻ አቲከም ግዛት ተደብቀው ስለነበር ነው፡፡
ተክለ ኢየሱስ ዋቅጅራ ወደ ጎጃም በተመለሱበት ወቅት የወቅቱ የጎጃም ገዥ ራስ በዛብህ ተክለሃይማኖት ሹም ሽር ሲያደርጉ፣ አለቃ ተክሌን የወንድማቸው የራስ ሥዩም (ኃይሉ) ወዳጅ ነው በሚል ስለአልሾሙዋቸው በመናደድ እንደገና ወደማይፈልጉት አገር ወደ ሸዋ ሊመጡ ሲሉ በመኳንንቱ ምክር ከጨሊያ እስከ ሟጨራ፣ የአዋባልን ሊቀካህናትነት ከነገደ በረከቱ ተሾሙ፡፡ ጣባ ኖላዊንም ተሹመው አስተዳድረዋል፡፡
ከንጉሥ ተክለሃይማኖት ሞት በኋላ ብዙም ያልደላቸው አለቃ ተክለ ኢየሱስ ዋቅጅራ ከመደበኛ የሥዕል ሥራቸው ሌላ የጎጃምን ታሪክ፣ የጎጃምን ትውልድና ካርታ በማዘጋጀት የደከሙ ጥበበኛ ናቸው፡፡
ይህንን ሁሉ የሠሩት በፈቃደ እግዚአብሔር እንጂ ዋጋ ተከፍሏቸው አይደለም፡፡ ለጎጃም በነበራቸው ቀናዒነት እንጂ፡፡ ቀናዒነታቸውንም ከጽሑፋቸው ጭምር ለመረዳት ይቻላል፡፡
አለቃ ተክሌ በመጨረሻ ዘመናቸው ባለቤታቸውን መፍታታቸው ሲያሳዝናቸው፣ በተለይ ንጉሥ ተክለ ሃይማኖት አገልጋይ እንድትሆናቸው የሰጡዋቸው ሴት አገልጋያቸው በ1916 ዓ.ም ስለሞቱባቸው በእጅጉ አዝነዋል፡፡
ሴትዬይቱ (በስም አሰራኝ ቤት ተክለ ሃይማኖት) ይባላሉ፡፡ አሽከሪቱ ጠባያምና ግብረ መልካም ስለነበሩ በእርሳቸው ሞት አለቃ ተክሌ በእጅጉ ሲያዝኑና ሲተክዙ ቆይተው በግምት በ1917 ዓ.ም እዚያው ደብረማርቆስ እንዳረፉ ይገመታል፡፡ ዲያቆን ኅሩይ ተክሌ የተባለ ልጅ እንደነበራቸውም ተመልክቷል፡፡
ወደፊት በታሪክ ሰነድነት የሚጠቀሱትን ግጥሞቻቸውን፣ ስለ ታላቁ የቅኔ ሊቅ ስለ መምህር ገ/ሥላሴ ክንፉና ስለሌሎች ቅኝት አደርጋለሁ፡፡ ቸር እንሰንብት፡

የአዲስ አበባ መስተዳደር አንድነት ፓርቲ የጠራውን የእሪታውን ቀን ሰልፍ አቅጣጫ ከቀየራችሁ እፈቅዳለሁ አለ

$
0
0

udj letter
ከዳዊት ሰለሞን

አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ መጋቢት 28/2006 ለጠራው ሰላማዊ ሰልፍ የእውቅና ደብዳቤ ለመስጠት ህጋዊ መስመሩን ለመከተል ተስኖት የቆየው የአዲስ አበባ መስተዳድር ዛሬ ማለዳ ለፓርቲው በላከው ደብዳቤ መጋቢት 28 በሌሎች መርሐ ግብሮች የተያዘ በመሆኑ ተለዋጭ ቀንና ቦታ እንድታቀርቡ ይሁን ብሏል፡፡ የፓርቲው አመራሮች ለተጻፈላቸው ደብዳቤ ምላሽ ለመስጠት በአሁኑ ሰዓት በውይይት ላይ ይገኛሉ፡፡

ጋዜጠኛ ሓገዞም መኮነን ተፈታ (አብርሃ ደስታ ከትግራይ)

$
0
0

ዜጠኛ ሓገዞም መኮነን (ወይን ጋዜጣ)
======================

Abrha Destaየቀድሞ የወይን ጋዜጣ አዘጋጅ ጋዜጠኛ ሓገዞም መኮነን ለሁለት ሳምንታት ያህል ደብዛው ካጠፋ በኋላ (ትናንት ደብዛው ስለመጥፋቱ ፅፌ ነበረ) ዛሬ በህይወት እንዳለ ደውሎ ገልፆልኛል። ጋዜጠኛ ሓገዞም ለሁለት ሳምንታት የጠፋበት ምክንያትና መንገድ ከመግለፅ ቢቆጠብም የህወሓትን የዓፈና ተግባራት ማጋለጥ ከጀመረና ከወይን ጋዜጣ አዘጋጅነት ከለቀቀ በኋላ በጠላትነት እንደተፈረጀ፣ ሚስጥር እንዳያወጣ እየተባለ በደህንነት ሰዎች ጥብቅ ክትትል እንደሚደረግበት፣ በሌሊት ሁለቴ የግድያ ሙከራ እንደተደረገበት፣ አሁንም ቢሆን የዉስጥ አዋቂ ከመሆኑ የተነሳ የቁም እስረኛ በመሆኑ ስራ ሰርቶ መብላት እንዳቃተው በስልክ ገልፆልኛል። የህወሓቶች የዓፈና ተግባራት የሚያጋልጥ መፅሓፉ በቅርቡ እንደሚታተም ተናግሯል።

ስለዚህ የጋዜጠኛ ሐገዞም መኮነን ቤተሰቦችና ወዳጆች ሐገዞም በህወሓቶች ክትትልና ዛቻ በአግባቡ መስራት ባይችልም በህይወት አለ።

ህወሓቶች እስካገለገልካቸው ድረስ ይጠቅሙሃል፤ የነሱ ባርያ ሁነህ እነሱን እስካገለገልክ ድረስ ቁሳዊ ጥቅም ይሰጡሃል። ነፃነትህ የጠየቅክ ግዜ ግን ወዮልህ! በህወሓት ቁሳዊ ጥቅም እንጂ ነፃነት መጠየቅ አይቻልም። ቁሳዊ ጥቅምማ ማንም የሰው አገልጋይ (ባርያ) ያገኘዋል። የሚፈለገው ነፃነት ነው። ነፃነት ከተነፈጋቸው ዜጎች ዋነኞቹ የህወሓት አባላት ናቸው። መቃወም አይፈቀድላቸውም፤ ይሄው እኛ ግን ችግር እየደረሰብን ቢሆንም በነፃነት መተቸት እንችላለን። የሚደርስብን ችግር እናውቀዋለን፤ እናም በሚደርስብን በደል አንምበረከክም። ነፃነት ይሻለናልና።

(ወይን ጋዜጣ የህወሓት ልሳን ነው)።

አንድነት –ህግን እያከበርን የማስከበር ኃላፊነታችንን እንወጣለን!! (ሰልፉ ለሚያዚያ 5 ተላለፈ )

$
0
0

አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ (አንድነት)
UNITY FOR DEMOCRACY AND JUSTICE PARTY
(UDJ)
ህግን እያከበርን የማስከበር ኃላፊነታችንን እንወጣለን!!
——————————————

ከአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ የአዲስ አበባ ምክር ቤት የተሰጠ መግለጫ በአዲስ አበባ ከተማ ከዕለት ወደ ዕለት እየተባባሰ በመጣው የማህበራዊ ግልጋሎት አቅርቦት እጥረትናአለመመጣጠን ምክንያት መንግሥት በተደጋጋሚ ጊዜ የእርምት እርምጃዎችን እንዲወስድ ቢጠየቅም የወሰደው እርምጃ ባለመኖሩ ፓርቲያችን መጋቢት 28 ቀን 2ዐዐ6 ዓ.ም ‹‹የእሪታቀን›› በሚል መሪ ቃል ታላቅ ሠላማዊ ሠልፍ እንደሚያደርግ ለህዝብ በመገናኛ ብዙሃን ይፋ ማድረጉ ይታወሳል፡

ሆኖም «የአዲስ አበባ ከተማ ሠላማዊ ሠልፍና ስብሰባ ማሳወቂያ ክፍልበመጋቢት 26 ቀን 2ዐዐ6 ዓም በቁጥር አ.አ ከስ/1ዐ/3ዐ.4/236 በላከልን ደብዳቤ ሠላማዊ ሠልፉን ለማድረግ በጠየቅንበት ቀን ተመሳሳይ የህዳሴ ግድብ ፕሮግራሞች ስላሉ ተለዋጭ ቀንእንድናቀርብ ጠይቆናል፡፡ በዚሁ መሠረት ለመጋቢት 28 ቀን 2ዐዐ6 ዓም ለማድረግ የያዝነውን ፕሮግራም ለማሸጋገር የህግ ግዴታ ስላለብን ለሚያዚያ 5 ቀን 2ዐዐ6 ዓ.ም ያዛወርን መሆኑንለኢትዮጵያ ሕዝብ በአክብሮት እንገልፃለን፡፡

አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ የአዲስ አበባ ምክር ቤት
መጋቢት 26 ቀን 2ዐዐ6 ዓ.ም
አዲስ አበባ

UDJ

 

 

 

 

ረዳት ፓይለት ሃይለመድህን አበራን ለማስመለስ የኢህአዴግ ልኡካን በጄኔቫ

$
0
0

ETH J

ረዳት ፓይለት ሃይለመድህን አበራን ወደ ኢትዮጵያ ለማስመለስ በአቶ አስመላሽ ወልደ-ስላሴ የተመራ ከፍተኛ የኢህአዴግ ልኡካን ቡድን ጄኔቭ፣ ስዊዘርላንድ ከርሞ ባለፈው ሳምንት ተመልሷል።

በፓርላማው የህግ እና የአስተዳደር ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ ሊቀ-መንበር የሆኑት አቶ አስመላሽ ወልደ-ስላሴ የተመራው ይህ ቡድን ከ March 13፣ 2014 ጀምሮ የስዊዘርላንድ መንግስት አካላት ጋር በሃይለመድህን ጉዳይ ላይ ለቀናት ተወያይቷል።  ስዊዘርላንድ ረዳት ፓይለቱን አሳልፋ እንድትሰጥም ቡድኑ ብዙ ሙከራ አድርጎ እንደነበርና ሙካራው ሁሉ ሳይሳካ መቅረቱንም ለማወቅ ችለናል።

ቡድኑ የስዊስ ፌዴሬሽን የህግ አካላትን ለማሳመን ካቀረበው ምክንያት ዋነኛው፣ ረዳት ፓይለት ሃይለመድህን አበራ የአእምሮ በሽተኛ መሆኑን እና ይህንንም ከራሱ ቤተሰብ አባላት እንዳረጋገጡላቸው ገልጸዋል።  የስዊዝ መንግስት ግን ጥያቄውን ውድቅ አድርጎታል። ለዚህም የሰጠው ዋነኛ ምክንያት፤ የሞት ፍርድን ተግባራዊ ለሚያደርግ መንግስት ማንንም አሳልፌ አልሰጥም የሚል ሲሆን ይህ ባይሆንም፣  በስዊዘርላንድ እና በኢትዮጵያ መሃል ተጠርጣሪ እስረኛን የማስመለስ ውል የለም ብለዋል።

በተያያዘ ዜና ወንድሙ ዶ/ር እንዳላማው አበራ እና በጀርመን የምትኖር እህቱ ሃይማኖት አበራ ጄኔቭ ድረስ በመምጣት የረዳት ፓይለት ሃይለመድህን አበራን ከሚገኝበት እስር ቤት ጎብኝተውታል። የስዊስ ጠበቆችም የፓይለቱ መብት እንዲከበር አጥብቀው እየሰሩ ይገኛሉ። መገናኛ ብዙሃን ላይ ሲደሰኩሩ የነበሩ አንዳንድ የኢትዮጵያ የህግ ባለሞያዎች እዚህ ጉዳይ ላይ እንዲተባበሩ ሲጠየቁ አሳፋሪ ምላሽ መስጠታቸውንም ጉዳዩን በቅርብ ከሚከታተሉት ኢትዮጵያውያን ለመረዳት ችለናል።

ረዳት ፓይለት ሃይለመድህን አበራ ባለፈው የካቲት 10፣ 2006 ዓ.ም. የኢትዮጵያ አየር መንገድ ንብረት የሆነውን ቦይንግ 767 አግቶ ጄኔቭ ስዊዘርላንድ ላይ በማሳረፍ እዚያው የፖለቲካ ጥገኝነት መጠየቁ ይታወሳል። የአለም ዜና ርዕስ ሁሉ ትኩረት ስቦ የነበረው ይህ ልዩ ክስተት የኢትዮጵያን የሰብአዊ መብት ሁኔታና የአስተዳደር በደል አደባባይ በማውጣቱ የገዢው ፓርቲ አባላትን እጅግ እንዳበሳጨ ይነገራል።

አንዳንድ መገናኘ ብዙሃን እንደገለጹት የአጎቱ ድንገተና ህልፈት ርዳት ፓይለቱን አስቆጥቶት ነበር። የሃይለመድህን አበራ አጎት፤ ዶ/ር እምሩ ሥዩም ህይወት በድንገት ማለፍ ለብዙዎች ያልተፈታ እንቆቅልሽ ነው።  ዶ/ር እምሩ ሥዩም የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ መምህር ነበሩ።

በአለም ዙሪያ ያሉ ኢትዮጵያውያን ወጣቱ ፓይለት ሃይለመድህን አበራን መደገፋቸውን እንደቀጠሉ ሲሆን በረዳት ፓይለቱ ስም የተከፈቱ ድረ-ገጾች እና የፌስቡክ መድረኮች ላይ ሰፊ ዘመቻ በማድረግ ላይ ይገኛል።

የስዊዝ ቴሌቭዥን በረዳት ፓይለት ሃይለመድህን አበራ ዙርያ አንድ ዘጋቢ ፊልም የሰራ ሲሆን ይህ ዘገባ ለትንሽ ግዜ እንዲዘገይ ተደርጓል። ዘጋቢ ፊልሙ አየር ላይ ያልዋለበት ምክንያት የረዳት ፓይለት ሃይለመድህን አበራ ጠበቆች እንዲዘገይ በመጠየቃቸው ነው ሲሉ ጉዳዩን የሚከታተሉት ኢትዮጵያውያን ገልጸዋል።

 

 

Viewing all 15006 articles
Browse latest View live