Quantcast
Channel: Ethiopian News | ዘ-ሐበሻ | Latest News Provider | News For All
Viewing all 15006 articles
Browse latest View live

ዕንባ! (ሥርጉተ ሥላሴ 27.03.2014 (ሲዊዘርላንድ ዙሪክ)

$
0
0

 

Cry-ethiopiaዕንባ የድረሱልኝ ጥሪ ነው። ዕንባ የችግር አዋጅ ነው። ዕንባ የፈተና ነጋሪት ነው።  ዕንባ የሰቀቀን ውስጣዊ እሳታዊ መግለጫ ነው። ዕንባ የመንፈስ ጭንቀት ረመጣዊ ተፋሰስ ነው፤ ዕንባ የጭምትነት ቁስለት እዢ ነው። ዕንባ የታመቀ ነበልባላዊ ጎመራ ነው። ዕንባ ውስጥን መለኪያ ነው። ዕንባን ለማስቆም ለመነሳት ሆነ፤ ለዕንባ ለመድረስ ደግሞ „ቅድመ ሁኔታ“ አያስፈልግም። እራሱ „ቅድመ ሁኔታ“ የሚለው ቃል ዕንባን ፈጽሞ አይመጥንም። ፍሉ ዕንባ ጥሪውን ሲያስተላልፍ ብስል ከቀሊል ሳይለይ ለሁሉም ሆኖ፤ ግን የሚማገዱት ጥቂቶች የቆረጡት ብቻ ናቸው። ሁላችንም መቆስቆሻ እንፈልጋለን። መቆስቆሻ ባያስፈልገው እንኳን ለዬግል የመንፈስ ምቾት አብዛኛዎቻችን እናዳላለን። ታዲያ ዕንባና ጥሪው ዬት – ከምን ይጠጉ? በዘመነ – ጠቀራ።

 

እጅግ የማከበራችሁ የሐገሬ ተስፋዎች፤ ይህን ዘመነ – ህማማት መመርምር ማገናዘብ አቃተን ማለት ባላችልም ጊዜው ያልደረሰ የግንዛቤ ችግር ግን ያለብን ይመስለኛል? ሰሞኑን የደንበር ጉዳይ በሚመለከት ተዘውትሮ የምስማው መሰረታዊ ጉዳይ አለ …. „የጎንደር መሬት፤ ጎንደሬ በሱዳን ተመታ“ ወዘተ …. ህም! እም! አደዋ የትግራይ ነበርን? ማይጨውስ የትግራይ ነበርን? ሐረርስ የሐረር ሰው ነበርን? ጎሬስ የኢሊባቡር ነበርን? ይህን መመለስ ስንችል ዛሬ መስጥረን የምንደልቅ እብኖች አይናችን ይከፈታል። ደንበሩ ሲጣስ ማህሉ ደንበር ይሆናል። የሱዳን ይሁን የግብጽ ዘመን የተሻገረ ፍላጎት የአውሮፓ ራዕይ ነው። ቀደምትን ሀገረ – ኢትዮጵያን ለማከሰም የተተለመ። ወያኔ የባንዳነቱን ተግባር እዬፈጸመ ስለሆነ ነገ እንደ ኩርድሾች የቁራጭ አፈር ለማኞች መሆን አይቀሬ ነው በዚህ ከቀጠለ። „የፉክከር ቤት ሳይዘጋ ያደራል“ ….. እንደሚባለው ….

 

ከዚህ ጋር ተያይዞ ያን ድንቅ ሰላማዊ የዕምነት እኩልነት ትግል „የድምጻችን ይሰማ እንቅስቃሴ“ ለማስቆም በምሽት የተበተነ በራሪ ጹሑፍ የሚያጨፋጭፍ ነበር። ባለቤቱ ማን ነበር? ተከትሎም ሳውዲ ላይ እህትና ወንድሞቻችን ተለይተው „ኢትዮጵያዊ“ እዬተባሉ በባዕድ ሀገር ደመ ከልብ ሲሆኑ ተባባሪው ማን ነው?  የኢትዮጵውያን ከጽንፍ እስከ ጽንፍና ቁጣ „ኢትዮጵዊነትን“ አጉልቶ ሲወጣ ከነፃነት ታሪካችን ፍቀት ጋር የተላተመው ዘመቻስ ማን ነበር ያዘጋጀው? አሁን ትናንት አንቦ አካባቢ የሚኖሩ ወገኖች አካላቸው ዓይኑ በቢላዋ ገብያ ላይ  አደባባይ  ወጥቶ እንደ ሀሞራቢ ዘመን ተቀጥቅጦ ሲገደል፤ እንዲሁም ወደ 600 አባወራዎች ተፈናቅለው ልምና ሲፈረድባቸው ሴረኛው ማን ነው? „የኦሮምያን አዬር ከባዕዳን ወረራ አድነነዋል ስለዚህም ቀጣይነቱ በእጃችሁ ነው ያለውና ጠብቁት“ ተብሎ የተሰጠው ግንጥል ስሜትስ ጅረቱ ዬት ይወስደናል? ይህ ጥቃትን እዬጠጡ መኖርስ አንድነትን ፈጥሮ ትብሺ ትብስ ብሎ ለመሰለፍ አቅምን ካለይግባኝ ወና ማደረጉስ ምን ሊባል ይሆን? በእርግጥም ዕንባው ጎርብጦናልን? መሮናል? አንገፍግፎናል? ከቶስ ይህ አረሮ ዘመንስ አልሰለቸንም ይሆን? ስደቱስ?! —-

 

ለወጡ ወደ ወያኔ ከመሄድ በፊት እያንዳንዱ የወገኔ ዕንባ – ዕንባዬ ነው፤ የአካሌ ሰቆቃ – ሰቆቃዬ ነው? የአካሌ ችግር – ችግሬ ነው የሚል ሁሉ በብራና ላይ የሚኩለውን መግለጫውን ይዋጠውና እራሱን ሰለመለወጡ በቅድሚያ ያረጋግጥ? ከራስ ሲነሱ ሙሉዑ ብቃት ያለው አቅም ይኖራል። እራስን መለወጥ ሲቻል አብነቱ ሃይልና ብርታት ያስገኛል። እራስን መቅጣት ሲኖር ድፈረት ይፈጠራል። እራስን ከስህተት አርሞ ይቅርታን ተላብሶ ሲነሱ እርግጠኝነት ይኖራል። በስተቀር ግን ውሃ ቅዳ ውሃ መልስ ነው። ክብሮቼ ወገኖቼ፤ ጠላትን መብለጥና በጠላት መበለጥ ዬት ላይ ስለመስከናቸው እስኪ እባካችሁን መዝኑት – በህሊና አደባባይ።

 

ኢትዮጵያ ሀገራችን ህዝቦቿ ከስሜን ወደ ደቡብ፤ ከደቡብ ወደ ስሜን፤ ከምስራቅ ወደ ምዕራብ፤ ከምዕራብ ወደ ምስራቅ በሽግሽግ – በውርርስ – ከቦታ ቦታ በመዘዋወር  - ተዋህደው የኖሩባት የአብሮነት ተምሳሌት ሀገር ናት። ይህ የዘመናት ሂደት የታሪኳ እንብርት ነው። የጥንካሪያዋ ምንጭም ይሄው ነው። እያንዳንዱ ልጅ ሲወለድ መክሊት ይዞ ይወለዳል። ስለሆነም የእያንዳንዱ መክሊት መስተጋብር ተዋህደው፤ በተፈጥሮ ተቀምረው፤ በጋብቻ አደብ ገዝተው፤ በማህበራዊ ኑሮው ተመክሮ መስኖ ለምተው፤ በፈቃደ እግዚአብሄር ተመርቀው ገናናዋን ታላቅ ሀገር ኢትዮጵያን ገነባ – መሰረተ።

 

 

እናት ሀገራችን ኢትዮጵያን የዛሬ ታላላቅ ሀገሮች በዲታነት በቁስ ቢበልጧትም፤ በመንፈስ ሀብታትና በውስጥ ብቃቷ ሆነ ጥራቷ እንዲሁም ከፈጣሪያዋ ጋር በአላት የቀረበ ግንኙነት ልዑቅ መሆኗን እነሱው እራሳቸው ጠንቅቀው ያውቃሉ – ባዕዳኑ፤ አፈር በቀል አንጡራ ጠላት ባንደዎችም ጭምር።  ኢትዮጵውያን የትም ይሁን የትም ውስጣቸው ፍሬ ዘለቅ ዕንቁ ነው። ሀገራቸው ኢትዮጵያ ወተቷን አጠጥታ እንደማሳደጓ፤ እሷም በልጃቿ አቻ የሌላት ሀገር መሆኗ ልብ ልክ ነው። ይህ ደግሞ በመንፈስ ብቃትና ብልህነት እያዬነው ነው። ሰለጠነ ከሚባለው ሀገር ከተማራው ዜጋ ያልተማረ አንድ ኢትዮጵዊ፤ በተፈጥሮ የፈጠራ ብቃቱ ሆነ አዳዲስ ሃሳቦችን በማፍለቅ አቅሙ ሆነ ችሎታው ዬት እዬሌለ ነው … አይገናኝም። ባያስመካም፤ ባያስኮራም ሥልጡኑ ጸጋው ሃብቱ ስለመሆኑ ግን መዘለል የለበትም።

 

የኢትዮጵዊነት የአብሮነቱ ፍቅሩም በሸቀጥ የተገዛ አለነበረም። መከባባሩ ገብያ አልነበረም ለአፍታ ሞቅ ብሎ የሚፈታ፤  ዬእናት ሀገራችን የኢትዮጵያ ታሪካዊ የአርበኝነት ጥንካሬዋ ምድራዊም አልነበረም። ዘንበል ብሎ የሚያደምጣት አምላክ ያላት ሀገር ከመሆኗ ላይ ነው – ረቂቁ አንድምታ። በህገ ልቦና አምላኳን አምና ከነበረችበት ዘመን ጀምሮ እምነቷ ሆነ ትምክህቷ በፈጣሪዋ ነው። በእኛ ዕድሜ እንኳን ዝናብ ሲጠፋ ለእስልም እምነት አባቶች ይነገራል። እባካችሁ „ድዋ“ ያዙ ተብሎ፤ መዕት ሲመጣም „ምህላ“ እንዲያዝ ለተዋህዶ አባቶች ይነገራል።

ደስታውንም ሀዘኑንም በእትብት ሀዲድነት ልባዊነት ጎልብቶ ገቢራዊ የሆነባት የጥቁር በዕት – ኢትዮጵያ እመቤት ነበረች። ወያኔ ሀገርን ለማፍለስ ሲነሳ ይህን አስፈሪ የውህደት ጥንካሬ መበተን ነበረበት – ለስትንፋሱ። በፋሳ ከሰሰከሰው።  ኮሳሳ ኢትዮጵያን አልሞ እዬሄደበት ነው። ዛሬ እኮ „ኢትዮጵያዊ“ ማለት ወንጀል ነው። አረንጓዴ ቢጫ ቀይን ሰንደቅአላማ መልበስ ያሳስራል። ያሰድዳል፤ ያስደበድባል። አሳሬ ህግም ተደንግጎለታል – ለሰንደቅአላማ …. የዘመን አረማሞ ወያኔ – ግባዕቱ መቼ ይሆን ?ወደ ሄሮድስ መሪው አፈር ሊያጫውት የሚሄደው በእጅጉ  ይናፍቃል —- መሬት ስትርድበት ወያኔን ማዬት —–

 

ጥንካረዋና ብርቷቷ የኢትዮጵያ  እንቅልፍ የነሳቸው የውጪ ኃይሎች አጋጣሚውን ይጠብቁ ስለነበር ብቃቷን ሊሸረሽር የሚችል ሥርዓት ለማምጣት ተግተው ሲሰሩ ኖሩ። በለስ ቀናቸውና አሁን የልባቸውን የሚያደርስ ሽፍታ ወያኔ በማግኘታቸው ትራሳቸውን ከፍ አድርገው በመተኛት የእርስ በርስ ጦርነት ሊያስነሱ የሚችሉ ጥቃቶችን ወሸኔ እያሉ፤ እያጀቡ እርዳታ ለሽፍታው ወያኔ ያጎርፋሉ።

አዬን አኮ ከሰሞናቱ ለአንዲት ወንዝ ገብ ክሪሚ ምን ያህል ጊዜ፤ መንፈስ፤ ገንዘብ፤ አቅም እዬፈሰስ እንደ አለ …..  የኃያላን ሀገር መሪዎች ከዙፋናቸው ወርደው ለክሪሚ ሲያሸበሽቡ ….ፕሬዚዳንት ፑቲን አርቀው መተንፈሻ ቧንቧ ለመንሳት ፊት ለፊት ወጥተው ሲፋለሙ …. በተጨባጭ ተመለከተን። እኛማ እንደ ሰው መታዬታችንም እንጃ ነው …. ያቺ ገናና የነፃነት አንባ፤ የአፍሪካ የነፃነት ተቋም፤ ኢትዮጵያማ …. ማን አስታውሷት? የተከበሩትን ኔልሰን ማንዴላ የነፃነት አባትነትን የሸለመች ድንቅ ሀገር – ኢትዮጵያ፤ መላ አፍሪካን ከቅኝ ግዛት ያወጣች የሞገዳማ ጥንካሬ ብቸኛ ባለቤት ምንጩ – ከሰው ፍጥረት መገኛ ከምንጩ ነበር።

 

ታዲያ እኛ ምን እንጠብቃለን? ስለ እኛ ዋቢ ጠበቃ የሚሆን ባዕድ ማግኘት ይቻላልን በዚህ አያያዝ? የኢትዮጵያን ታላቅነት ለማን ሲመቸው ነው? ይህነን መርምሮ ማግኘት እንዴት ይሳነን? ይህንን ብናውቅ እኮ የምናቀርበው የድርድር ቅድሚያ ሁኔታ ባልነበረ? ሰው ልህሊናዊ ጉዳዩ የምን „ቅደመ ሁኔታ ነው“ ዕንባው ቅርባችን አይደለንም?! ብናውቅስ የምንመካበት ሰበብ ባልነበረ? ለስበብ የምናጠፋው ጊዜም ባልኖረ? ለጥሎ ማለፍ ሽኩቻም የምናቃጥለው ቆራጣ ጊዜ ባልኖረን? ያገባኛል ለምንልለት „ኢትዮጵያዊነት“ ዕንባ ጥሪውን በምን ክህሎት ይሆን ምላሽ ሰጥቶ ለስኬት የሚበቃው? ማናቸውም የወያኔ ጥቃት የእኔ ጥቃት ብሎ የመንፈስ መስማማት እንዴት ይፈጠር?! ግልጽነት ዘመኑን እንዲመራን መቼ ይሆን ይለፍ https://www.zehabesha.com/amharic/archives/13892 የሚያገኘው?!

 

እኔ እንደ ሥርጉተ እማስበው ማሸነፍ ከወያኔ በፊት እራስን ነው። ሙሉ ትጥቅና ስንቅ የጎደለው መንፈስ እሽሩሩ እያልን አብዛኞቻችን እስከመቼ? …. ጥቃቱ ይቀጥላል …. ዕንባውም ይጎርፋል …. ሽንፈቱም ይናኛል ….. እግዚአንሄር እኮ ነው በኪነጥበቡ ጠብቆ ያቆያት ኢትዮጵያን እንጂ እንደ እኛማ መትበስበስ እንደ ወያኔ የጥፋት ዕወጃ ቢሆን አልነበረችውም።

 

እጅግ የሚያሰፈራ ነገር ፊት ለፊት ደግሞ አለ። ….  በዬቦታው ዜጋ አይደለህም እዬተባለ የሚነቀል፤ የሚሰቀል መንፈስ ብድሩን ለመመለስ ከተሰናዳ የሚያቆመው አይኖርም። አንድ የማወቀውን ነገር እስኪ ልንገራችሁ። ጎንደር የጓንግን ወንዝ ተከትሎ በአርማጭሆና በጭልጋ መካከል „የጋላ አገር“ የሚባል አለ። ስለ ቃሉ ይቅርታ እኔ የሰጠሁት አይደለም። በጣም ብዙ ቦታዎች በተለያዬ ሁኔታ ዘመኑ የፈቀደው ስያሜ ተሰጥቷቸዋል። ለነገሩ አሁን የእስራኤላውያን ስም ሥልጣኔ ይሁን አላውቅም ሥራዬ ብለን ተያይዘነዋል። የባዕድ ፊደላትንም እንዲሁ፤ ድምጸቱ ፍሰቱ የእኛ ያልሆኑ እንደ እራስ አድርገን ተቀብለናል። „ጨጸ“ በቁቤኛው የሉም። እነዚህ ከነድምጻቸው ደግሞ ከእኛ ተፈጥሮ ጋር ኖረዋል በአንድ ምድጃ።

ስለሆነም የባዕዱ ሲመጣ አናውቅህም ብለው ትርጉም አልባ ያደርጉታል ወይንም የስያሜው መንፈስ ጥንዙልና ፍዙዝ ይሆናል። „ጸጋዬ“ የታላቁ የቅኔው ልዑል ሥያሜ ነው። ልዩ ስጦታ፤ መንፈሳዊ ሃብት፤ የውስጥ ክበረቴ፤ የማንነቴ ረድኤት ከአምላኬ ብቻ የተሰሰጠኝ እንደማለት ነው። ይህን ተፈጥሯዊ ጌጣችን እያፋለሰው ግን ተቀበልናል በዚህ ዘመን። ስለሆነም  የቦታው ስያሜ እኔ ተቀብዬ የጻፍኩት አይደለም – ከቀደመው ዘመኑ የሰዬመው እንጂ።

 

…. ለማንኛውም በዚህ አካባቢ ለዘማናት የኦሮሞ ልጆች ተዋልደው ተጋብተው ኑሯቸውን መስርተው ያሉ እጅግ ብዙ ወገኖቻችን አሉ። ዋልድባ ገዳም ሲመሰረት ሆነ ከግራኝ ጥቃት በኋላም አባቶቻችን የመጡት ከሽዋ ነው። ሌላ ጊዜ ታሪኩን እምለስበታለሁ። የዘመነ መሳፍንት ታሪኩ መሰል ነው፤ የክፈለ-ጦሮች ሰራዊት አሰፋፈርና ኑሮም በመሰል ሁኔታ ተከናውነዋል። አሁን ጎንድር ከተማ አዬር ማርፊያ አዘዞ ጡረታ ሰፈር ወዘተ በጣም በርካታ ቅይጥ ሁኔታ ነው ያለው፤ በጣሊያኑ ንድፍ አስፈፃሚ በወያኔ ደግሞ „በታላቋ ትግራይ“ ዶክተሪን ጎንደርና ወሎ ተመሳሳይ የህዝብ ሰፈራ ተከናውኗል። ይህ ሁሉ እሳት ቢነሳ ማነው ማጥፋት የሚችለው ነው ጥያቄው? መተላለቅ ብቻ።

 

… እሳት የሚተፋ ዕንባ ይንቀለቀላል … ሁሉም ነገር የዶግ አመድ ነው የሚሆነው። አብሶ የቆላማ አካባቢ ነዋሪዎቹ ተዋጊዎች ናቸው። ቦታውም እራሱ ተዋጊ ነው። እንቅልፍ ወስዶታል ብላችሁ „አያ እከሌ“ ብላችሁ ውድቅት ሌሊት ላይ ብትጠሩት ትራሱ ያዘጋጀውን መሳሪያ መዥልጦ ብድግ ነው …. ቆለኛ ተረጋግቶ ተኝቶ አያውቅም፤ ከትዳር አጋሩ ይልቅ አቅፎ የሚተኛው መሳሪያውን ነው። አልሞም አይስትም።  ቆቆች ናቸው።  የቆለኛ ሴቷ እራሷ አለባበሷ እንደ ደገዋ አይደለም። ነጠላዋን በቀኝ እጇ አውርዳ ታደገድገዋለች። ስትቀመጠም ቁርጢጥ ብላ እንጂ ዘርፈጥ ብላ ሙሉ አካሏን አደላድላ አይደለም። ዝግጁ ናት …. ለማናቸውም ጉዳይ … ይህ እንግዲህ የአንድ በጣም ውስን አካባቢ ምስል ነው። ሌላውም አካባቢ መሰል ጉዳዮች አሉ። …. ዕንባው ፈንድቶ እሳት መትፋት ሲጀምር የሚያስቆመው አጋዚ የለም።

 

በሌላ በኩል መቼም ሽማግሌ ግራጫማ መካሪ የጠፋበት ጠፍ ዘመን ላይ እንገኛለን። ነገር ግን በትእግስት – በአርምሞ – በተደሞ ሆነው የሚኖሩት ኢትዮጵውያን በደሉ ሲባዛ፤ እንዲህም ሲከረፋ የነገ ተስፋዎች ወጣቶቹ በውስጣቸው ሽበት ያበቅሉ ናቸውና የተገባ አይደለም፤  ግፉ በዝቷል ወገኖቻችን እዬተገፉ ነው በማለት፤ በነቂስ እየተለቀሙ ሀገር አልባ፣ መሬት አልባ፣ ዜግነት አልባ፣ ማንነት አልባ፣ መኖሪያ አልባ ሆኖ ከሚጠቃው „አማራ ብሄረሰብ“ ጎን ይቆማሉ።  በተጨማሪም አማራ አካባቢዎች እትብታቸው የተቀበሩውም ማዕከላዊ ግንዛቤ ያላቸው ወደ ጎሳዊ ስሜትና ግንዛቤ አንወርድም በማለት እራሳቸውን በተዕቅቦ ያቆዩትም ቢሆኑ የለዬለት ድርሻቸውን ለመወጣት ይቆርጣሉ …. ይወስናሉ። ሲበዛ ይገለማል። ሲከርም ይበጠሳል። የማይቻለውን አስኪ ሻግት ተቻለ —- ቀጣዩ መራራ ኮሶ፤ አሰንጋላ እንዳይሆን ሙሴዎችን በትዝብት ይጠብቃል።

 

ፍትጊያው – ትግሉ – ጦርነቱ – ተከትሎ ሀገርና ህዝብ፤ ትውልድና ታሪክ፤ ከሁሉ በላይ አብሮነትና ፍቅር አፈር ድሜ ይግጣሉ። ኢትዮጵያ ወያኔ የሳላት ኢትዮጵያ ብጥቅጥቅ  እንድትል ታጥቆ የዶለተባት ኢትዮጵያ አይሆኑ ትሆንና …. የወያኔ ፍላጎት ሳይሸራረፍ ተግባር ላይ ይውላል። የጣሊያንም ህልም ይሳካል። የባዕዳን ራዕይ ይመሾራል። ግን እኛ ሀገርና መሬት አያስፈልግንም? አትናፍቅም ያቺ ውድ ሀገር ኢትዮጵያ!?!

 

ለመሆኑ መሰሉ እርምጃ ቢወሰድ፤ በእጥፍ ድርብ ቢወራረድ፤ ይህ ለነገ ይጠቅማል ወይ? ሀገር አልባነት – አፈር አልባነት – ኩራት አልባነት – መመለሻ ቤት አልባነት – ዘር አልባነት – ውርስ ቅርስ ትውፊት አልባነት – መሳቂያነት  መኖር ወይንስ ምን ይባል ይሆን? …. ወላጅ አባቴ ሲበዛ ጭምት ነበር። ተራማጅም አስተሳሰብ ነበረው – ያው መምህርነት ልዑቅ ሙያ ነውና። አልፎ አልፎ  ምን እዬታዬው እንደሆነ አላውቅም  በልጅነቴ ደጋግሞ ያዜመውና ይወደው የነበረ ስንኝ ነበር ሙዚቀኛው ማን እንደ ነበር አላውቅም … ይቅርታ

 

„እናት አባት ሲሞት በሀገር ይለቀሳል

እህት ወንድም ሲሞት በሀገር ይለቀሳል

አክስት አጎት ሲሞት በሀገር ይለቀሳል

ሀገር የሞተ እንደሆ ወዴት ይደረሳል?“

 

ሀገር አልባነት ውርዴት ነው፤ አደራ መብላት ነው፤ አንገት መድፋት ነው፤ በራስ መተማመን እንደ አወጣ ገብያ ላይ አውጥቶ መሸቀጠም ነው ፤ ሰንደቅአላማን መጠቅጠቅ ነው። ይህ የሚያረመጠምጥ ከሆነ መከራን ለማስቆም እራስን መለወጥ በእጅጉ ለምን ያቅተናል?  ለእኔ ይህ ገና ነው። ፍላጎቱ ብቻ እንጂ መሳሪያውም ማሳውም አልተሰናዳም። በደሉም ሰርስሮ ውስጣችን ገና አልገባም፤ ለዚህም ነው ነገሮችን ሁሉ ሳንመረምር እንደወረደ እያዋህድን መንፈሳችን የሚታወከው። ቁጣችን ቁስለትን የማያተርፈው። ቁሰለት ትርፍ ከሆነ መሸነፍ ያከትምለታል።

 

መሬት ላይ ያለው እውነተኛ ነገር በወያኔ ላይ ድል ያደረገው እኔ የማልደግፈው ድርጅት ከሆነ ጆሮ ማን ሲሰጠው። ቃለ ምልልስም ከሆነ ማን ቁብ ሰጥቶት ሲያዳምጠው። ማንስ ውጤቱን ሲያደንቀው  – ሲያከበረው። ወገኖቼ – የኔዎቹ  ቢያንስ „አክሱም ለጋንቤላው ምኑ ነው?“ ሲሉ ሄሮድስ መለስ ሲሳለቁ ያን ጊዜ በነፍስ ወከፍ የነፃነት ትግሉ ቤተሰቦች ቆሰልን። ግን ይህነን ንጹህ ቁስለኝነት እኛ ሸፍነን ወይንም አከናንበን ወይንም ሸጉጠን ከምናስተናገደው የዛሬ ጉድ ጋር ፊት ለፊት ተቀመጠን እስኪ እንመዝነው …. ሃቅን አንፍራ! ቢያንስ ለህሊና። ለእኛ ሲሉ ባሩድ ኑሯቸውን የነጠቀው፤ ትዳርና ቤታችን፣ ልጅና ኑሯቸውን ወጣትነታቸውን፤ የማይጠገበውን የልጅነት ክፈለ ጊዜያቸውን ለካቴና ለፈቀዱትም ትንሽ እንሰብ …. ምስጋናው፤ ዬክበር ቀኑ ማሰናዳቱ መልካም ሆኖ ሳለ ውስጥን አሸንፎ ወቅቱ ለሚጠይቀው ሁኔታ መገዛት አለመቻል ጥሬ ነገር ነው – ጠጠር። ፍልሚያ —-

 

ሌላው  ሳቢያ ተኮር መሆናችንም ሊመረመር የሚገባው መሰረታዊ ጉዳይ ነው።  ጊዜ እንዲበላ የምንፈቅድለት እንደ እውነቱ ከሆነ ለሳብያ ነው። ስምምነቱም – ድርድሩም – ውሉም – ቃል ኪዳኑም ለሳቢያ የሰገደ ነው። ለዚህም ነው አድሮ ጥጃ የሚኮነው። „ቂም ይዞ ጸሎት ነው“ ነገሩ። አቅም ማጣትን የፈቀድንለት እኛ እንጂ ዕንባማ የዘወትር ጥሪው አቅም ለድል እንደሚያበቃ ጠንቅቆ ያውቃል። ለድል የሚየበቃው ወሳኝ ነገር የችግሩን ምክንያት ማወቅ ነው።

 

አጀንዳውም መሆን ያለበት ይሄው ነው። አቅምም – ጊዜም – ገንዘብም – መደመጥም ያለበትም  ምክንያታዊ ጉዳይ ላይ መሆን አለበት። ይህ ከሆነ ከሽንፈት ጋር ሳይሆን የቀጠሮ ዝርዝር መርኃ – ግብራችን ከማሸነፋችን ሚስጢር ጋር ይሆናል። ማለምና መከወን ፍሬ ማዬትም ይሆናል ሰነዳችን። ይህን ነው በውስጣችን መዋጥ ያለብን አምክንዮ።  የመደራጀትም አስኳል፣ የሩጫውም መስመር ዬድካሙም ዲካ መለካት ያለበት ከዚህ አንጻር ይመስለኛል። ይህ ከሆነ አቅም ሳይባክን፤ ወቅትም ሳያመልጥ፤ ምቹ ጊዜም ሳይሾልክ ሁሉ ነገር ምክንያታዊ ከሆነው ፍላጎታችን ላይ ከዋለ ነገን ማግኘት ይቻላል። ይህ ማለት መቁረጥ መወሰን መሆን መቻል ሦስቱ ሥላሴዎች ማሸነፍን አምጠው ይወልዳሉ …. በተረፈ አንድነት ከአንቦ ለተፈናቀሉ የዕንባ ቤተኞች ለወገኖቻችን ብቸኛ መጠለያ ጥግ ዕንባን አድማጭ በመሆናችሁ አመሰግናችኋለሁ። እንደ እናታቸው ጓዳም ቤት ያፈራውን ማካፈላችሁ ውስጥን ይመረምራል።

 

ክውናዬ ለዛሬ  „ከቶ ዬት ይሆን ዬፍላጎታችን ሴሉ ያለው?“ ብዬ በ23.03.2014 በጻፍኩት ላይ የተከበሩ አቶ ምስክር እውነቱ የሰጡት ገንቢ አስተያዬት ይሆናል። „ዲቃላ አታድርጊው“ እሺ ብያለሁ የእኔ ጌታ። ሲቸገር ነው እንጂ እኔም አልወድም። 17 ዓመት ተግቼ ስጽፍ አይደለም ጋዜጣ ላይ የዋሉት፤ ያልዋሉትን ጌጠኛ ቃላትም ተግቼ መጠቀሜ ለቋንቋው ካለኝ ቀናዒነት ነው። መጻህፍቶቼም በሙሉ ይህን መርህ የተከተሉ ናቸው። ነገር ግን አማርኛ ቃላት የሌላቸው ፊደላት አሉ። „ጰ ና ፐ“ ከሁለቱም የሚፈጠሩ ቃላት የትውስት ናቸው። በተጨማሪም ከዘመን አመጣሹ ኢንተርኔት ጋርም ተዛመጆች አቻቸውን በአማርኛ ማግኘት ይቸግራል። ቃላት እንደ ሥልጣኔ ይሰደዳሉ፤ ይወራረሳሉ፤ ከዚህ ሌላ በሥነ – ግጥም ዘርፍ ገጣሚ በአንድ የግጥም እርእስ ሥር የፈለገውን ቋንቋ ቀላቅሎ የመጠቀም ሙሉ ዓለምዓቀፋዊ መብት አለው። ሌላው ፎንቱ ደቀቀ ስላሉት የድህረ ገጹ ባህሪ ነው። ኢትዮ ዛሬ እኮ ከዘሃበሻም የከሳ ፊደላትን ይጠቀማል። እጅግ የማክብረዎት የሀገሬ ልጅ እኔም እማነበው በመነጸር ነውና እርሰዎም እንዲሁ ያድርጉ ። በተረፈ እኔ በምመራው ድህረ ገጽ ያሉትን ገባ ብለው የቀደሙትና ዋጋቸው ያልቀነሱትን ይመልከቱ፤ በፒዲኤፍ የተሰሩ ናቸውና ማዬት ይችላሉ። www.tsegaye.ethio.info  በርከት ያሉ አውዲዎችም አሉ፤ ጊዜ ካለዎት የዳምጧቸው። በተለይ „ተስፋ“ ላይ የመስቀል ባዕልን ምክንያት በማደረግ በ2001 የተሰራ ልዩ አውድዮ አለ …. ይወዱታል። „ስለ ድርጅት“ ጽንሰ – ሃሳብም „ማዕዶት“ ላይ … እርሰዎን ይጠብቃሉ – በተጠንቀቅ ….

 

የኔዎቹ ላበቃ ነው ፍቅርን ከውስጤ ሰጥቼ። መቆዬት መልካም ነው የምለው ኢትዮጵያን ለማዬት ካበቃ ብቻ ነው ለእኔ።

 

የዕንባ ቋሚ ጠበቃ መዳህኒዓለም ብቻ ነው።

እልፍ ነና እልፍነታችን እልፍ እናድርገው – በተግባር!

 

 

እግዚአብሄር ይስጥልኝ።

 

↧

↧

የፓልቶክ ቦለቲከኞችን ማን ሃይ ይበለን (ቶኩማ አሸናፊ)

$
0
0

 

   PALTALK የፓልቶክ ታዳሚ ነኝ ። ሃሳቤን በፓልቶክ ክፈሎቸ ማሰተላለፍ አይከብደጘም። ግፋ ቢል በቀይ መታሰር ሲበዛም ( ባውንስ) ሃሳብን በቁም መግደል  አለበለዚያም  ወያኔ ደርግ ጽንፈኛ አድርባይ ሻቢያ ግነቦት 7 ኦነግ ጎሰኛ ብቻ አንዱን ስም ተለጥፎብኝ እንደምወጣ ሂደት አስተምሮኛል። የፓልቶከ ቦለቲካ ያስተማረኝ አንዱ መጥፎ ገጽታ ነው።በፓልቶከ ክፍሎች አንዳንዴ የመነጋገሪያ አጀንዳ ሲጠፋ የተለያዩ መጣጥፎቸን ማንበብ የተለመደ በመሆኑ እራሳቸውን አጀንዳ ለማድረግና ምናልባትም ጊዜና ጉልበታቸውን ገንዘባቸውንም ጭምር መሰዋእት በማድረግ ለትግሉ አስተዋጽኦ ለማድረግ ደፋ ቀና ለሚሉ ወገኖቼ እራሳችንን እንድናይና የሳይበሩን አለም በተሻለ መንገድ እንድንጠቀምት ለመገፋፋት በብእሬ ትንሸ ለመኮርኮር ተነሳሳሁ። ማይክ የቸበጠ ሁሉ ወይም በሎቢ ላይ ቃላት የወረወረ ሁሉ ፖለቲክኛ በሚመስልበት  የፓልቶከ መድረክ ቦለቲከኛውን ከፖለቲከኛ መለየት አስፈላጊነቱ ወቅታዊ ነው።  

በመጀመሪያ ፖለቲከኞች የምላቸው በኣንድ ህበረተሰብ ውስጥ የሚታዩትን ፖለቲካዊ አኮኖሚያዊና ማህበራዊ ችግሮች ለመፍታት የፖለቲካ ስርኣቱን ለመለወጥ ወይም ለማሻሻል በግንባር ቀደምትነት የተሰለፉና ኣላማቸውንም ለማስፈጸም በጠራ የፖለቲካ ኣስተሳሰብ የታነጸ መነሻና መድረሻ ባለው የፖለቲካ ኣጀንዳ ስር የተሰባሰቡ ግለሰቦችን ነው፤፤ የፖለቲካ ስራ የሚሰራውም የማንኛውም ስርኣት ኣንቀሳቃሽ ህዝብ በመሆኑ ፖለቲከኞች ከህዝብ ጋር ያላቸው ግንኙነት ወሳኝ ነው።

ለዚህ መነሻ ሃሳብ ያነሳሳኝ ከጊዜ ወደጊዜ አየዘቀጠ የመጣው  የዲያስፖራው በተለይም የሳይበሩ ኣለም “ቦለቲከኛ” መብዛት ነው፤ ቦለቲካ የሚለውን ቃል የሰማሁት ድሮ ልጅ ሆኜ በጣም ብዙ የሚያወሩና የሚያወሩት ነገርም እውነትም ዪሁን ውሸት ነገር ግን ሌላውን ለማሳመን የሚጠቀሙበት ቁዋንቁዋ የኣድማጭን ቀልብ የሚስብና ሃሰቱን እውነት እውነቱንም ሃሰት ኣድርጎ የማቅረብ ችሎታ ያላቸውን ሰዎች” እሱ እኮ ቦለቲከኛ” ነው ሲሉት  ትዝ ይለኛል።

ታዲያ ዛሬ ቴክኒዎሎጂ በፈጠራቸው የመገናኛ ብዙሃን በደምጽ በሚሰሙት ራዲዮ ቴለቭዥን ፓልቶኮች በኣንድ ጊዜ በበዙ ሰዎች ሰለሚደመጥ ቦለቲከኞችን ከፖለቲከኞች ለመለየት የተቸገርንበት ለመሆኑ በእርግጠኝነት ለመናገር  ይቻላል ፡፡ መነሻዬ የዲኣስፖራው ፖለቲከኞች መድረክ የሆነውን ፓልቶክ ክፍሎችና ተዋንያን ቦለቲከኞችን በመሆኑ በዚሀ ጽሁፌ እሱ ላይ አተኩራለሁ።

አሁን ባለንበት ሁኔታ የኢትዮጵያ ፖለቲካ የሚጠነሰስበት የሚፈጭበት የሚጋገርበት መድረክ ፓልቶክ ሆኖኣል ማለት ይቻላል። የሃገሪቱ ባለስልጣናት ወያኔ ኢሃደግ ደጋፊዎች ኣባላትም ጭምር  ጀምሮ ተቃዋሚ ነን የሚሉ የፖለቲካ ድርጅች መሪዎች ተገንጣዩም አስገንጣዩም ኣንድነት ባዩም ጠባቡም ትምክህተኛውም ኣፍቃሪ ሃይለስላሴና ደርግ ስርኣቶችም ጭምር በኣጠቃላይ የኢትዮጵያ ጉዳይ ያገባናል የሚሉ የዲያስፖራውም ሆነ የሃገር ቤቱ ፖለቲከኛም ቦለቲከኛም የሚሳተፍበት ዋነኛ መድረክ ሆኖኣል ፥፥ በፓልቶክ ከፍሎች የእምነት የማህበራዊ ጉዳዮች የፖለቲካ ተደማምሮ ከ ሶማሊያ ቀጥለን በሁለተኛ ደረጃ ላይ የምንገኝ የመሆናችን ምክንያቱ ብዙ ምርምር የሚያስፈልገው ሳዪሆን የብዙ ፈርጅ ችግርተኞች አንደሆንን የሚያረጋግጥ ነው፥፥ የሁዋላ ቀርነት መለኪያም ነው፤፤ የዲሞከራሲ እሴት ደሆች መሆናችንም ነው ፥፥ ዝብርቅርቅ ታሪክ  ኣስተሳሰባችን ላይ የቀረጸው ዝብርቅርቅ ኣመለካከት ነው ፥፥ ይህ ራሱን የቻለ ርዕስ ስለሆነ ወደፊት በሰፊው ለማሳየት እሞክራለሁ፥፥የኣሁኑ ተኩረቴ ግን የፖለቲካ ከፍሎችን ነው፥፥

ለፖለቲካ መወያያ መድረክነት የተፈጠሩ ከፍሎችኣደረጃጀት የተለያየ ነው፥ እንደሃገር ቤቱ በቈዋንቁዋ ላይ የተመሰረቱ ክልሎች በስም ጭምር የኣሮሞ የትግሬ የኣማራ  የሃረሪ   ወዘተ  የክልል ፓልቶኮች

በሃሳብ ከኢትዮጵያ ተገንጥለው ነጻ መንግስት የመሰረቱ ክፍሎች  ሚኒለከ ጅኖሳይድ

የስርኣቱ ዋና ደጋፊ የሚባሉ የሚታወቁ እንደ ገዛ ተጋሩ  Eprdf  ካናዳ ኢትዮ ሲቪሊቲ  በግልጽ የሚታወቁ

በተቃዋሚች በኩል የተወሰኑ የፖለቲካ ድርጅቶች ኣስተሳሰብ የበላይነትን የያዙባቸውና በርካታ የድርጂት ደጋፊዎችን ያቀፉ ዲሞክራሲ በገደብ የሚሉ

እንደ ኢካዲኤፍ ( ግንቦት ፯ ደጋፊዎች የሚበዙበት)

ቃሌ ( መድረክ መኢኣድ ኢዴፓ ኢህአፓ ደጋፊዎቸ የተደበላለቁበት )

EFND (ኢህአፓ) የመሳሰሉ

በሌላ በኩል የሁሉንም ኣስተሳሰብ እናንሸራሺራለን የሚሉ ነገር ግን ኣብዛኛው ስርአቱን ሂሳዊ ድጋፍ እንሰጣለን በሚል የተዋቀሩ በፖለቲካ የሃይል አስላለፍ መመዘኛ ግን የሰርኣቱ ደጋፊዎች  ጎልተው የሚታዩባቸው እንደ ቅንጂት ስዊዘርላንድ ፡ ኢትዮ ዲኣስፖራ አይነቶችና በመጨረሻም ተጀምሮ አስከሚጨረስ ተቃዋሚንት እነጂ የት ነው ያሉት የሚያስብልና የስድብ ትምህርት ቤት ይመስል የነበረው  ደብተራ ክፍሎች (አሁነ ግን ስድበ ተቅንሶአል)

በየክፍሎቹ ውስጥ የሃገራቸው ጉዳይ የሚያንገበግባቸው ነገር ግን ሃሳባቸው የበላይነትን ይዞ ያልወጣና ኣሰባሳቢ ኣመለካከት ስር ያልሰደደ በመሆኑ በድምጻውያን ቢዋጡም በርካታ ቅን ዜጎችና በሃሳብ የበሰሉ ዜጎች ለፓልቶኩ ፖለቲካ ዉበት ናቸው ። እጂግ በዝተው የሚታዩት ግን ቦለቲከኞች ናቸው፥፥

የቦለቲከኞቹን መገለጫ ከማየቴ በፊት ስለ ክፍሎቹና  የኣንዳንድ ቦለቲከኞች nick name ትንሽ ልበል፥፥ ኣብዛኛዎቹ የፓልቶክ ከፍሎች ስምና ማነነታቸው ኣይጣጣምም ፥፥ ለምሳሌ ኢካዴፍ ቃሌ ቅንጂት ስዊዘርላንድ  ደብተራ ሊክስ  ሞረሽ  ጀኖሳይድ ወዘተ ስማቸውና ውስጣዊ ማንንታቸው የተለያዩ ናቸው።

የፓልቶክ ታዋቂ  ስሞች ለምሳሌ ኣባመላ፡ ሎሬት ጸጋዬ፡ ደብተራው የመሳሰሉ  ስመ ጥር የሃገራችን ታላላቅ ሰዎች ስም ሲሆን ስሙን የያዙት ሰዎችና የፓልቶክ ባህሪያቸው ፈጽሞ  አይገናኝም ፥፥ሎሬት ጸጋዬ  ገብረመድህን በስሙ የሚቀርበውን ፓልቶከኛ  የስድብ ቃላት ከሞት ተነስቶ ቢያዳምጥ ፊታውራሪ አባመላ በዘመናችን የፖለቲካ መለኝነት ምን እንደሚመስል ቢሰሙ ተመልሰው መሞትን ይናፍቁ ነበር፥፥ የፓልቶክ ፖለቲካ የበሺታ ምንጭ ሃላፊነትና ተጠያቂነት የጎደለው በውጭ እየኖረ ሃገር ቤት ያለው ጥቅም የሚነካበት የሚመስለው በኮምፒውተር ጀርባ ያለ ፈሪ ቦለቲከኛ ነው።

ወደ ዋናው ነጥብ ልመለስና በእኔ እምነት የፓልቶክ ቦለቲከኞች  መገለጫ

፤ እውነትን ሽምጥጦ መካድና ሃሰትን እውነት ኣስመስሎ የማቅረብ ችሎታ

፥ የፖለቲካ ግጭቶችን ልዩነቶችን ፍጹማዊ ማድረግ 100% መደገፍ ወይ መንቀፍ

፤ በመሰረታዊ ጥያቄዎች ፕሪንስፕልስ  ላይ በየጊዜው ተገለባባጭ ኣቍም መያዝ (ኣካሄድ ሊለዋወጥ ይችላል

፤ የውይይት ቁዋንቋቸው (ቶን) የማያደርጉትን የሚያደርጉ መስሎ መቅረብ

፥ ፥የኢትዮጵያ መጻኢ እድል ወሳኝ ሃይሎች ሆኖ መታየት ብቸኛ ኣክቲቪስት ተንታኝ መስሎ መታየት

፤በፓልታልክ ኣበባ የሚፈነድቁ ለራሳቸው የሚሰጡት ግምት የተቆለለ ቦለቲካ መሆኑ ኣበባ ባዩ ቁጥር ደምጻቸው ከፍ እያለ የሚሄድ የሎቢ ጉበኞች

፤ የኣስተሳሰብ ድሀነትን በስድብ ባለጸግነት ለማካካስ የሚፈለጉ ስድብና ፖለቲካ የተቀላቀለባቸው

፥  ያነበቡትን ሁሉ በኢትዮጵያ ፖለቲካ ውስጥ መደንቀር የሚፈልጉ ከነባራዊ  ሁኔታ የተፋቱ

፥  ሌላው በተናገረው ላይ ብቻ ለመናገር ማይክ ለመያዝ የሚሽቀዳደሙ የራሳቸው ምንም ግባት የሌላቸው

፤ የፖለቲካ መሰረቱ ህዝበ መሆኑን ያልተረዱ በህዝብና በፖለቲካ ድርጅት መካከል ያለውን ኣንድነትና ልዩነት ለመገንዘብ የማይፈልጉ ዘረኛ ሆነው ዘረኝነትን የሚያወግዙ የ ጎሳ ፖለቲካን በኣፍ የሚጠየፉ  ነገር ግን ወሳኝ ነገር ሲመጣ የዘር ጉዋዳ የሚያንጎዳጉዱ።

፤ ስለ ዲሞክራሲ ስለፍትህ ስለ እኩልነት የሚሰብኩ በተግባር ዲሞክራሲን የሚገሉ ፍትሃዊ ወይይትን የሚገድሉ እኩልነትን የሚንዱ

እነዚህ በፓልቶኩ ፖለቲካ በየትኛውም ክፍል የሚታዩ የቦለቲካው መገለጫዎች ናቸው፤፤ ኣንዳንዱ ብዞዎችን ባህሪያት ያሙዋላል አንዳንዱ በተወሰኑት ስር ይወድቃል፥፥ ፖለቲከኛ ሳይሆኑ ቦለቲከኞች ይበዛሉ ያልኩት ከዚህ በመነሳት ነው፥፥ሽፋኑ ደግሞ ሃገር ወዳድነት ነው፤፤ በእርግጥም ብዙው ሃገሩን ይወዳል  ያፈቅራል ። ታዲያ መውደድና ማፍቀር በኣግባቡ ካልተያዘ ኣደጋም እንዳለው መረዳቱ ደግሞ ኣስፈላጊ ነው፥፥ ብዙ ኣፍቃሪዎች ፍቅረኞቻቸውን  ገድለው ለምን አንደገደሉ ሲጠየቁ ስለሚያፈቅራቸው መሆኑን ይናገራሉ ። የነሱ ብቻ እነዲሆኑ ስለሚፈልጉ። የአንዳንዶቻችንም የሃገር ፍቅር እንደዚያ ይመስላል። ሃገርን በግል ኣፍቅረህ በግል ችግርዋን ኣትፈታም፥፥

ዛሬ የደረስንበት የፓልቶክ ፖለቲካ ደግሞ ቅጥ ኣምባሩ የጠፋ ሆኖኣለ ፥፥ በተለይ የሲቪሊቲ ባለቤትና በፓልቶክ የሚታውቀው ቦለቲከኛ ኣባ መላ(ለጊዜው የፓልቶክ ስሙን እጠብቅለታለሁ የፓልቶክ መጠሪያው ነውና ) በ ፓልቶልክ ፖለቲካ ውስጥ እራሱንም እየገነባ የፓልቶክ ታዳሚውም እየገነባው መጥቶ እነሆ በራሱ ቦለቲካ ሆኖኣል፥፥ የግለሰቡን ማነነት ወይም ሰብእና ቁመት ውርደት ሆድ ኣፍንጫ መነጸር ወዘተ ወይም የጥንት ማንነቱን ለመመርመር ከአንድ ወር ቦለቲካ ሆኖኣል፥፥በበኩሌ ፖለቲከኛ ሳይሆን ቦለቲከኛ ለመሆኑ በመመዘኛዎቼ ኣስቀምጬ ኣብዛኛውን መስፈርቶቼን ከሚያሙዋሉት ኣንዱ መሆኑን ማረጋገጥ ይቻላል ፥፥ እስቲ እያንዳንዱ እራሱን ይመዝን፥፥ ሰለኣባመላም ወር የፈጀ ውይይት የሚያደርጉ ወገኖቼንም በዚሁ መመዘኛ ኣስቀምጡዋቸው፥፥

የኣባመላ የኣቋም ለውጥ በኣንድ የፖለቲካ ድርጅት ቢሆን የኣቁዋም ለውጡን መመርመር በሱም ላይ ጊዜ ማጥፋት የተገባ ነው፥፥ ምክንያቱም ሃገርን እንመራለን የሚሉ  የፖለቲካ ድርጅቶች ኣቍዋም ለውጥ በሃይል ኣሰላለፍ ላይ ትልቅ ጫና ስለሚያሳርፉ በፕሮግራማቸውም ጭምር ሚዛን ስለሚቀይር ነው፥፥ የሲቪሊትይ ኣቋም ለውጥ ወይም የኣባመላ ኣቋም ለውጥ ከዲያስፖራው ቦለቲካ ኣልፎ በኢትዮጵያ  ፖለቲካ ላይ ተጽእኖ ያሳድራል የሚል ኣመለካከት ካለ ኣሁንም የቦለቲከኞች ችግር ነው የሚሆነው::  እዚህ ላይ ኣባመላን ያነሳሁት የወቅቱ የሳይበሩ ቦለቲካ ሰለሆነ፡ አበመላም ከአርብ እስከእሁድ ታዳሚውን በራሱ ቦለቲካ ዙሪያ ደፋ ቀና እያለ የትላንት ሰዳቢዎቹን የማሰባሰብ ዘመቻ ስለ ያዘ ነው ።

በበኩሌ ኣባመላ ኣቋም ለውጫለሁ ያለባቸውን ፍሬ ጉዳዮች ትላንትም የምደግፋቸው ዛሬም አንዲራመዱ የምፈልገው ነው።

፩፡  በኢትዮጵያ ብሄራዊ ጥቅም ያለመደራደር

፪፥ የሻቢያን ቀንደኛ ጠላትነት ማወቅ

፫፥ ለሃገር የሚጠቅም ልማትን የፖለቲካ መጠቀሚያ ኣለማድረግ።መሰረተ ሃሰቡ እሰማማዋለሁ ወያኔ ኢሃዴግ ልማት ልማት ሰልሚል ተቃዋሚ ከሆንኩ የልማት ተቃዋሚ መሆን ኣለብኝ ወይም

ተቃዋሚነት ምንም ዪሁን ምን የምትቃወመውን መቶ በመቶ መቃወም አለብህ የሚል ጨለምተኛ አመለካከት የትም አያደረሰንም።

የሰርአቱ ደጋፊዎችና አባመላም ጭምር አንድ ሰሞን መለስ ማለት አባይ ነው፡ ራእዩ ነው ብለው በአባይ ስም መለስን ከነምናምኑ እንድንደግፈው ሲያደርጉት የነበረው ፕሮፓጋንዳ አልሰምር ሲል አሁን ደግሞ አባይን አለመደገፍ የግብጽ ወዳጅ መሆን ነው በሚል ተራ ፐሮፓጋነዳ ተተክቶአል።

የኣባይ ጥቅም ላይ መዋል ከጥንት ነገስታት ጀመሮ የህዝብ ፍላጎት የነበር በአጼ ሃይለ ስላሴ

በሎኔል መንግስቱም አባይን ለመገደብ ፍላጎቱና ምኞቱ አልነበረም ማለት አይደለም።

በርግጥም ብሄራዊ ጥቅማችንንና ፖለቲካውን እንዴት እንደምናጣጥመው በወያኔ አኢሃዴግ ብቻ ሳይሆን በአንዳንድ ተቃዋሚ ሃይሎችም ችግር አለ። የፖለቲካ ስልጣን ጥያቄ ብሄራዊ ጥቅምን ጭምር የሚገዳደረው ከሆነ አጥፊ ፖልቲካ ነው። አንዱና ዋነኛው ስርአቱን ምንቃወምበት ለ ፖለቲካ ስልጣን ብሎ የሃገሪቱን ጥቅም አሳልፎ ሰጥቶአል የምንለው። ታዲያ በዚሀ ረገድ ተቃዋሚው የአባይ መገደብ ላይ የሚታዩ ቴክኒካዊ ችግሮችን ከዘላቂ ብሄራዊ ጥቅም ጋር አለ ማጋጨት ተገቢ ይመስለኛል። በሌላ በኩል የአባይን ቦንድ መግዛት ይጠቅመኛል ያለ ሊገዛ ያልጠቀመው ሊተው መብቱን ማክበር ተገቢ ይመስለኛል። ምክንያቱም ከብሄራዊ ጥቅም ባሻገር ከአንቨስትመንት ጋርም የተያያዘ በመሆኑ ነው፥፥ኢንቨስትመንት ደግሞ  በፓልቶክ ወይም  በፖለቲካ ድርጅቶች የሚወሰን ሳይሆን ግለሰቡ ያዋጣኛል ያተርፈኛል በሚለው መስክ ነው ኢንቨስት የሚያደርገው። ኣሜሪካ ውስጥ ቤት ገዝቼ ኢንቨስት ኣደርጋለሁ የሚል ኣሜርካ ኢንቨስት ማድረጉን ለማንም አንደማያማክር ማለቴ ነው፥፥ ጉዳዩን ወያኔ ኢሃዴግ ቦለቲካ ሲያደርገው ፤ እኛም ቦለቲካ ኣናድርገው ነው፥፥ ይህ ማለት የወያኔ አሃዴግን ጩሀት ኣብረን እንጩህ ማለት ኣይደለም ፥፥

ብሄራዊ ጥቅምን ወይም ውያኔ ኢሃዴግ የስልጣኑ ዋና ማራዘሚያ የሆነውን የብሄረሰብ ችግር ወደ ጎሳ ፖለቲካ ለጥጦ ጥዋትና ማታ ብሄር ብሄረ ሰብ ስለሚል በመሬት ላይ ያለውን ችግር በመካድ የብሄረ ሰቦችን ችግር ማንሳት አያስፈልግም የሚል ወይም ያነሳን እንደ ዘረኛ መቁጠር አንድነትን ያመጣል ማለትም አይሆንም። የተጠቀሱትን ነጥቦች ያነሳሁት አባ መላን ቦለቲካ ለማድረግ ሳዪሆን አባ መላ በነዚህ ጥያቄዎች ዙሪያ ማለትም

የሻቢያን ጠላትነትና ወዳጀነት

የልማትና እድገት ጥያቄ ክዚሁ ጋር የአባይ መገደብ አሰፈላጊነት ክብሄራዊ ጥቅም አንጻር ማየቱንና የብሄራዊ ጥቅም አጀንዳ ደግሞ በየጊዜው ምትቀያይረውና ከፖልተካ ድርጂቶች ጋር በሚኖር ጸብና ኩረፊያ ላይ የተመሰረተ አቅዋም አለመሆኑን ለማሳየት ነው። አባ መላ የሚወቀስበትም የብሄራዊ ጥቅም አጀንዳን አንደፈለገ ማሽከርከሩ  የኣባይ መገደብን እንደ ፈለገ ሲቦተልክበትና የብሄረ ሰብ ጥያቄና ቺግሮቹን የተለያየ ኣቋም መውሰዱ ነው። ከዚህ በተጨማሪ የተቃዋሚወን ጎራ ኣስተካክለዋለሁ በሚል ኣጉል ጀብደኝነት የተለያዩ የፖለቲካ ኣጀንዳዎች ለምሳሌ የኣማራውንና የኦሮሞውን ኢሊት አስታርቃለሁ; አለም አቀፍ የተቃዋሚ ግራስ ሩት እመሰርታለሁ ;የኣለም ኣቀፍ አርዳታ ቡድን ቃለኣቀባይ ሆኜአለሁ በሚል ተስፈንጣሪ ፖለቲካና የራስ መካብ ቦለቲካ ውስጥ ተዘፍቆ የፓልቶክ ቦለቲከኞቺን እያንጫጫ ያለው ።

ሌላው አባመላ ወስጃለሁ የሚለው አቅዋም ወደመሀል ፖለቲካ መጥቻለሁ

የሚል ነው:: ወደመሀል ፖለቲካ መምጣትና ወደነበሩበት አቁዋም መመለስ ይለያያሉ።  የመሃል ፖለቲካ ለሀገራችን  ይበጃል የሚል እምነት ካላቸው ወገኖች አንዱ ነኝ። አገራችን ካለቺበት ወሰብሰብ ቸግር ልተወጣ የምትችለው ጫፍና ጫፍ የተጣረዘ ፖለቲካ ሳይሆን የብሔራዊ መግባባት ፖለቲካ መስፈን አማራጭ የሌለውና ወደመሀል መምጣት ከሁሉም አቅጣጫ  ሊበረታታ ይገባል የሚል አምነት አለኝ ወደመሀል ሰንተር ፖለቲክስ መምጣት ማለት ግን በነባራዊ አውነታዎች ላይ ተመርኩዞ ያሉትን የተለያዩ ቅራኔዎች ቅደም ተከተል አስቀምጦ በሂደት ሊፈቱ የሚችሉትን ጊዜ ሰጥቶ ከሁሉም  በላይ መፋጠጥን አስቀርቶ የመቻቻልና ተፋላሚ ቡድኖች ሁሉ ተጠቃሚ የሚሆኑበት መፍትሄ ማቅረብ እንጂ አንዱን ደግፎ ሌላውን በመርገምና በመኮነን ላይ  ያተኮረ ፖለቲካዊ አካሄድ አይደለም :: አባመላ ሲፈልግ ተቃዋሚውን ሃይልና ግለሰቦችን ሲፈልግ መንግስትና ደጋፊዎቹን ሰብእና የጎደለው ተራ ስድብ እያወረደ ለዲያሰፖራው የፓልቶክ ቦለቲከኞችና ፓልቶክን መደበሪያ ላደረጉ ብቸኞች መዝናኛ ከመሆን ያለፈ ፋይዳ አይኖረውም።

ከዚሁ ጋር ሌሎች ቦለቲከኞቻችን  ወደመሀል መምጣትን ከግራ ዘመሙ የፖለቲካ አስተሳሰብ በተቀዳው አድርባየነት ስፈርጁት ይታያሉ :: ዓለም በተለያዩ ቅራኔዎች በተወጠረችበት በዚህ ዘመን ፖለቲካዊ  ቅራኔዎችን ለማርገብና በተለያየ መልኩ ሴንተር አቅዋም አንደመሳሪያ ሆኖ ያገለግላል :: በፖለቲካ የተነሳ የብዙ ሕዝብ ህይወት የሚቀጥፉ ፖለቲካዊ ችግሮችን መፍቻ

አንዱ ዘዴ ነው ።ይህም አቅምን ለመገንባትና የሃሳብ የበላይነትን ለመያዝ የሚያስችል አትሞስፈር መፍጠር ማለት ነው ። ወደ መሃል መምጣት” ምን ተቃዋሚ አለና” እየተባለ አይደለም። ቀስ በሎ ወደ ነበሩበት ለመመለስም መሸጋገርያ መንገድ ሊሆን አይችልም።

ሰለዚህም አባ መላ የስርአቱ ደጋፊ ነኝ የማለት መብቱ የተጠበቀ ሲሆን የፖለቲካ

ተርሚኒዎሎጂዎችን ይዘታቸውን  ለራስ እነዲጠቅሙ በመመጠን ግራ የተጋባወን የድአስፖራ የፓልቶክ ቦለቲከኛ ማስጨብጨብ ከተራ ፕሮፓጋንዳ ውጭ ሊሆን አይችልም ።

ከላይ የውቅቱ የፓልቶክ  ቦለቲካ ምን አንደሚመስል አንዱን ክስተት ብቻ  በመሰረታዊ ጥያቄዎች ዙርያ ለማሳየት ያህል አንጂ ሰለአባመላ ብዙ ለመጻፍ ፈልጌ አይደለም :: የችግሩን ተጠያቂነትም ለአባመላ ለመስጠት አይደለም።የሚወራው ሰለአባመላ ሆድና ቁመና ሰለ ቀድሞ ማንነቱ ከመሆኑም በላይ ፓልቶከኛ ተቃዋሚው ትግሉን ወዴት እየወሰደው ነው ? የሚለው የዝቅጠት ፖለቲካ እነዲያቆም ለመገፋፋት ነው። ከሁሉም በላይ የስርአቱ ደጋፊዎች ምን ያህል እንደወረዱ የሚያሳየው ተመለሰልን ብለው የተፉትን ምራቅ ለመላስ አንድ ሳምንት ጊዜ እነኩዋን ለአባመላ የማሰቢያ ጊዜ አለመስጠታቸው ነው፡፡ ቦለቲካ ማለት ይህ ነው።

የፓልቶክ ቦለቲከኞች  አስደናቂ ባህርይ  አባመላን በሀሳብ ዙሪያ ሳይሆን ልክ የአባ መላ የአቀራረብ ባህሪይ ያለው የአራዳ ልጅ ተፈልጎም ይሁን ራሱ ፈልጎ ስለ አባመላ ህይወተ ፖለቲካ በአራዳ ቁዋንቁዋ  ከ800 በላይ ቦለቲከኞች ቁጭብለን ሰናዳመጥ አጃኢብ ያሰኛል :: በርግጥ በተነሱት የአቅዋም ጥያቄዎች ላይ አጀንዳ ይዘው የተወያዩ ከፍሎች የሉም ማለት አይደለም : በእንዲህ አይነቱ ውይይት ላይ የሚሳተፉት እድምተኞች  ግን  ቁጠራቸው በጣም ትንሽ ነው :: ይሄም የሚያሳየን ዲያሰፖራው ፓልቶክን የመማሪያና የሃሳብ መለዋወጫ  ለትግሉና ለሀገርም የሚበጁ የሃሳብ መፍለቂያዎች ከመሆን ይልቅ የቦለቲካ ኮሜዲያን ማፍለቂያ መድረክ እንዳይሆን ከልባቺሁ ለለውጥ መሳሪያነት ለመጠቀም የምትፈልጉ ወገኖች በያላችሁበት እራሳችሁን ፈትሹ። እንፈትሽ።

በመጨረሻም ከጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ አባባል ልዋስና ” ኑ እንዋቀስና ኢሃዴግን እናፍርሰው”

 

ቶኩማ አሸናፊ

↧

ያልታሰረው ማን ነው?? (ከአንተነህ መርዕድ)

$
0
0

 

ud-bahirdar-demo

UDJ – Bahir Dar Demonstration

ሰሞኑን አንድ ኢትዮጵያዊ በቶሮንቶ የህሊና እስረኞችን ለመዘከር በግሉ አዳራሽ ተከራይቶ የአንዱዓለም አራጌን “ያልተሄደበት መንገድ” የሚለውን መጽሃፍ ለሽያጭ በአቀረበበት ቦታ ተገኝቼ ነበር። በዚህ አዳራሽ አንዱዓለምን፣ እስክንድርን፣ ርዕዮትን …ወዘተ ለመዘክር ብለው የተሰባሰቡ ሰዎች ብዛት ስመለከት “በእውነቱ እስረኞች እኛ ነን ወይስ እነ ዓንዱአለም?” የሚል ጥያቄ ጫረብኝ። አገርን ያህል ትልቅ ነገር ከራሳችን የፖለቲካና የግል ጠባብ ፍላጎት ዙርያ ቀንበበን ልንከተው ስንቸገርና አልሆንልን ሲል ደግሞ እርስ በርሳችን ስንጎነታተል አሁን አለንበት የመከራ ዘመን እንድንቆይ በራሳችን የፈረድን መሆኑ ግልጽ ይሆናል።

ትንሹን ህይወታቸውንና ጠባቡን የግል ፍላጎታቸውን በትልቁ ለሚያይዋት ኢትዮጵያ የሰውትን ወንድሞቻችንን ልናስታውስ በሚደረግ እንቅስቃሴ ሁሉ ብዙዎቻችን በተረባረብንና የነሱን ከባድ መስዋዕት በትንሽ በትንሹ በተጋራናቸው ነበር። እውነቱ ግን ያ አይደለም። ለብዙዎች የእንቅስቃሴያችን ማዕከል ሁሉ “እኔ” ስለሆነ ከዚያ የተለየን ማውገዝ፣ ማደናቀፍ፣ አለመተባበር…ተግባራችን የሆነ ይመስላል።

አንዱዓለም እንዳለው ከዚህ በፊት ያልተሄደበትን የመቻቻልና የመከባበር መንገድ መጀመር የጊዜው ጠቃሚ እርምጃ ነው። ይህ ሁኔታ መጽሃፍ ቅዱስ ላይ የዮሃንስ ወንጌል ምዕራፍ 8 ቁጥር3 እስከ 11 “ጻፎችና ፈሪሳውያንም በምንዝር የተያዘች ሴት ወደ እርሱ አመጡ በመካከልም እርስዋን አቁመው መምህር ሆይ ይች ሴት ስታመነዝር ተገኝታ ተያዘች። ሙሴ እንደነዚህ ያሉትን እንዲወገሩ በህግ አዘዘን። አንተስ ስለእሷ ምን ትላለህ? አሉት።….ከእናንተ ኃጢአት የሌለበት አስቀድሞ በደንጋይ ይውገራት አላቸው።…እነሱ ይህንን ሲሰሙ ህሊናቸው ወቀሳቸውና ከሽማግሌዎች ጀምረው እስከ ኋለኞች አንድ አንድ እያሉ ወጡ” ይላል። ከኛም መካከል ህሊናው የሚወቅሰው ካለ ከተሳሳተ ድርጊቱ መቆጠብ አለበት። በዚሁ መጽሃፍ ቅዱስ የሉቃስ ወንጌል ላይም “በወንድምህ ዐይን ያለውን ጉድፍ ስለምን ታያለህ፤ በራስህ ዐይን ግን ያለውን ምሰሶ ለምን አትመለከትም?” ሲል ይደግመዋል። እያንዳንዳችን የምንከተለው መንገድ ትክክል ሊመስለን ይችላል። የሌሎችን ሆነ የእኛን ትክክለኝነት የሚዳኘው ተግባራችንና ጊዜ ነው። እስከዚያው ግን መከባበርና መተባበርን የመሰለ ትልቅ ነገር የለም።

ፖለቲከኞች፣ የሃይማኖት ሰዎች ሆነ ተራው ግለሰብ የራሳቸውን ሳይሆን በሌሎች ሰዎች ስህተት ላይ ብቻ ማተኮር ሲጀምሩ የውድቀታቸው መነሻ ይሆናል። ማንም ሰው ሲሠራ ሊሳሳት ይችላል። መጥፎው ነገር ከስህተት አለመማር ነው። ስህተቱን በጸጋ የሚቀበልና የሚያርም ትልቅ ነው። በእስልምና እምነትም ሃዲስ ላይ (በትክክል መጥቀስ ባልችል ይቅርታ ይደረግልኝ) እንዲህ ይላል “የማያውቅ ሆኖ የማያውቅ መሆኑን ማወቅ የማይፈልግ ቂል ስለሆነ ሽሸው። የማያውቅ ሆኖ አለማወቁን የሚያውቅ ከሆነ ልጅ ነውና አስተምረው። የሚያውቅ ሆኖ አዋቂ መሆኑን የማያውቅ ከሆነ ቀስቅሰው፤ ተኝቷልና። አዋቂ ሆኖ አዋቂነቱን የሚያውቅ ከሆነ ጥበበኛ ነውና ተከተለው” የብዙዎቻችን ባህሪ ባንዱ ሁሉ የሚካተት ነውና ቦታችንን ማወቅና እርምጃችንን ማስተካከል የተገባ ነው። ስለሆነም የታሰሩ ወንድምና እህቶቻችን የተሸከሙት እዳ ከግላችንና ከቡድናችን ፍላጎት በላይ አገራዊ ስለሆነ ከመጎነታተል፣ ከመከፋፈል ወጥተን አገራዊ ስፋት ባለው አላማ ዙርያ በጋራ መቆም ይኖርብናል።

ወደ ተነሳሁበት ርዕስ ልመለስና “ኢትዮጵያ የብሄረሰቦች እስር ቤት ናት” የሚለው ለትናንቶቹና ለዛሬዎቹ ጠባቦች መንደርደርያ ማዕከላዊ ሃሳብ ቢሆንም ደጋግመው እንደሚናገሩት ይህንን ብሂል በሃቅ ለብሄር ብሄረሰብ ነፃነት አልተጠቀሙበትም። ያ ቢሆን ምንኛ በታደልን። ድርጊታቸው ግን ተቃራኒ በመሆኑ ኢትዮጵያን ወደ ገሃነምነት ቀይረዋታል።

በአምደጽዮን፣ በፋሲለደስ፣ በቴዎድሮስ፣ በዮሃንስ፣በምኒልክ፣ በሃይለስላሴ ኢትዮጵያ ዴሞክራሲ ማበብ ነበረበት ብሎ የሚያስብ አእምሮ ቅንነት አለው ብለን አንጠብቅም። እነዚህ ነገስታት ግዛታቸውን ለማስፋት፣ በስልጣናቸው ላይ ለመቆየት ባደረጉት እንቅስቃሴ ጭካኔ የተሞላበትን መንገድ መሄዳቸው ግልጽ ነው። በዴሞክራሲያዊ ስርዓት እናስተዳድራለን ብለውም አያውቁምና የሚጠብቅም አልነበረም። ዳኝነታቸው ርህራሄና ፈሪሃ እግዜብሄር ያለበት እንዲሆን ሁሌ ባያከብሩትም ይናገራሉ፤ ህዝቡም ይጠብቃል።

ዛሬ በትናንት ታሪክ ታስረን፣ ለዚያ የከፋ ድርጊት ከመካከላችን ተጠያቂ ፍለጋ ስንኳትንና አጽም ለማውጣት መቃብር ስንቆፍር የሁላችን መቀበርያ አዳዲስ መቃብር እየተዘጋጀልን መሆኑን ዘንግተናል። በተለይም በዴሞክራሲ ስም እየማሉ የገዙን ሁለቱ ስርዓቶች ማለትም ደርግና ወያኔ ካለፉት ነገሥታት በባሰና በዘገነነ ሁኔታ ጨካኞች ናቸው። አገሪቱንም ወደ ሙሉ እስር ቤትነት የቀየሯት እነዚህ አምባገነኖች ያለፉትን አገዛዞች በኮነኑበት አንደበት የራሳቸውን ትልቅነት ከመስበክ ወደ ኋላ አላሉም። በነዚህ አገዛዞች “ኢትዮጵያ የዜጎች ሁሉ እስር ቤት ናት” የሚለው ከፀሃይ የደመቀ ዕውነት ነው።

ይህን ዓለም ያወቀውን እውነት በመካድ የትናንቶቹ አምባገነኖች መንግስቱ ኃይለማርያምና ፍቅረስላሴ ወግደረስ የነሱ አገዛዝ ፍትህ የሰፈነበት፣ ዴሞክራሲ የሞላበት የሚያስመስል ስንክሳራቸውን አሳትመው እንደጲላጦስ እጃቸውን ሊታጠቡ ይዳዳቸዋል። ፍቅረስላሴ “እኛና አብዮቱ”ባለው መጽሃፉ ቢያንስ ለታሪክና ለህዝብ ክብር ትንሽ የቅንንነት ጥፍጣፊ እንኳ ጨምሮበት ‘ሰርተን ያለፍነው ስህተት ይህ ነበር፣መጪው ትውልድ ከእኛ ስህተት ተምሮ መልካም አገር መገንባት አለበት’ የሚል እውነት በመጠኑም ይዞ ይቀርባል ተብሎ ሲጠበቅ ለብቻቸው ያዝዟቸው በነበሩት ሠርቶ አደር ጋዜጣ፣አዲስ ዘመን፣ የዛሬይቱ፣ ሄራልድ፣ ሬድዮና ቴሌቪዥን ላይ ሲያደነቁሩን የኖሩትን ፕሮፓጋንዳ ሃያ ሶስት ዓመታት ሲያመነዥከው ቆይቶ ለህትመት ሲያበቃ የህዝቡንም የማስታወስ ችሎታ መናቁን አሳይቷል። ፍቅረስላሴ በእስር ባሳለፈው ሃያ ዓመታት ወደ ኋላ በትዝታ መለስ ብሎ የሄዱበትን መንገድ ሁሉ በመቃኘት ወደ እውነቱ ቀርቦ መገኘት ሲገባው ሲታሰር ተኝቶ ሲፈታ የነቃ ይመስል። የኢትዮጵያ ህዝብ ቀድሞ ያለፈበትን የመከራ ዘመን ሆነ አሁን እየደረሰ ያለበትን ጭቆና ዳግም እንዳይመለሱ በመታገል ላይ እያለ ፍቅረስላሴ ባንኖ በመንቃት ድሮ የጻፈውም ሜሟር እንዳለ ይዘምርልናል። “በማይጨው ጊዜ የደነቆረ ስለማይጨው ሲተርክ ይኖራል” እንዲሉ ስልጣን ሲለቁ እንደደነቆረና ከዚያ ወዲህ የኢትዮጵያ ህዝብ በምን አስተሳሰብ ላይ እንዳለ ለመገንዘብ ያልታደለ መሆኑ እንድናውቅ ያደርጋል።

ፍቅረስላሴ አሁን ድረስ የሚያመልክበትና በፍርሃት የሚያሸረግድለት መንግስቱ ኃይለማርያም ብቸኛ አላማው የሆነውን የስልጣን ጥማቱን ለማርካት የህዝቡን ለጋ ወጣቶች ብቻ ሳይሆን በእድሜና በልምድ መከበር የሚኖርባቸውን አዛውንት ኢትዮጵያውያንን፣ ጓደኞቹን ሳይቀር ተራ በተራ ሲያርዳቸው ቆሞ ሲንቀጠቀጥ፣ ማረጃ ሰይፍ ሲያቀብል እንዳልነበረ የነሱን የፍጅት ዘመን ከወያኔ ጋር እያነጻጸርን እንድንናፍቀው በተዘዋዋሪ ሊነግረን ይሞክራል።

የኢትዮጵያን ጠላቶች በየፈፋው ያርበደበዱት እነጄኔራል ታሪኩ ላይኔ፣አማን አንዶም፣ አምሃ ደስታ፣ ፋንታ በላይ ….ወዘት ዛሬ ተርፈው የተንሸዋረረ ታሪክ ሊነግሩ እንዳሉት በፍርሃት አልራዱም። አምባገነኑን አምባገነን ነህ እያሉ ነው የሞቱት። ታሪካቸውን ራሳቸው ባይናገሩም አብዛኛው ኢትዮጵያዊ ያውቀዋል። ሲያከብራቸውም ይኖራል። እነሱንና አገሪቱ የገደሉት የታሪክ ዝቃጮች ስለሥራቸው ምን ቀለም ቢቀባቡ ማንነታቸውን ሊደብቁ አይችሉም።

ለመሆኑ የአስራ ሰባት ዓመቱ የ“እኛና አብዮቱ” ውጤት ምን እንዳስገኘ ፍቅረስላሴ ይዘረዝረዋል? ህዝቡንና አገሪቱን ቀፍዶ አስሮ ለወያኔና ለሻዕብያ ያስረከበው ማን ነው? “ወርቅ ሲያነጥፉለት ፋንድያ የሚመርጥ” ብሎ መንግስቱ ሃይለማርያም የሰደበውን ህዝብ አንተም በተጠያቂነት ታቀርበው ይሆን?

አዎ ኢህአፓዎች፣ መኢሶኖች፣ወዝሊጎች፣ ማልሬዶች፣ ሻዕብያዎች፣ ወያኔዎች፣ ኦነጎች…..በዚች አገር ውድቀት አውቀውም ሆነ ሳያውቁ አስተዋጾ ማድረጋቸውን ለማወቅ ህዝቡ የፍቅረስላሴንና የጓደኞቹን ምስክርነት የሚፈልግ አይደለም። ምንም እንኳ ይህ ነበር የኛ ድርሻ ለማለት ድፍረቱን ባያገኙትም ህዝብና ታሪክ የሁሉንም አስተዋፆ አይረሳውም።

ቀበሌዎችን፣ የጦር ካምፖችን፣ መኖርያ ቤቶችን፣ ትምህርት ቤቶችን ሁሉ ወደ እስር ቤትነት የቀየረ፣ ወላጆች የልጆቻቸውን  አስከሬን ለመቀበል የተገደሉበትን ጥይት ዋጋ ያስከፈለ፣ አልቅሰው እርም እንዳያወጡ የከለከለ፣ አዛውንቱን ኃይለስላሴን ያለፍርድ ገድሎ መቃብራቸው ላይ መፀዳጃ ቤት የሰራ…ወዘተ ይህን ሁሉ ያደረገ የደርግ ስርዓትና መሪዎቹ የሌሎችን ያነሰ ስህተት የሃጢያታቸው መጠራረጊያ ፎጣ ሊያደርጓቸው የሚያስችል የሞራል ብቃት የላቸውም።

የመሬት አዋጅን እንደትልቅ ድል ደጋግሞ ማንሳቱም የሚገርም ነው። ብዙ ኢትዮጵያውያን የተዋደቁለ የመሬት ጥያቄ በደርግ ሆነ በወያኔ አልተመለሰም። አዋጁ መሬትን ከመሬት ከበርቴዎች ነጥቆ ገበሬውንና መሬቱን የአምባገነኖች ንብረት ነው ያደረገው። ወያኔዎችም ካባታቸው ደርግ ደህና አድርገው ተምረዋልና  ኢትዮጵያዊ የመሬት ባለቤት የሚሆነው “በኢህአዴግ ሬሳ ላይ ነው” ሲል መለስ ዜናዊ ደምድሞታል።

ከገበሬው የወጣን ነን የሚሉት የደርግ አባላት ሆኑ ለገበሬው ቆሜያለሁ የሚሉት ወያኔዎች በካድሬዎቻቸው አማካይነት ንብረቱና ራሱን ገበሬውን የራሳቸው የግል እቃ፣ በቤቱም ውስጥ እስረኛ አድርገውታል። በህብረት እንዲያርስ የተገደደውና በችጋር የተጠበሰው የአርሲ ገበሬ “በናንተ ህብረት እርሻ ያተረፍነው በርሃብና በተባይ ማለቅን ነው” ብለው ብልቃት ሙሉ ቅማል ለደርግ ባለስልጣን ማሳየታቸውን በወቅቱ በቦታው የነበርነው ጋዜጠኞች ተመልክተናል። ይህን እውነት በአብዛኛው  አገሪቱ ለሥራ በተዘዋወርሁባቸው ወቅት ባይኔ አይቻለሁ።

ደርግ የጀመረውን የአፈና መንገድ ወያኔዎች በረቀቀና በሰላ መልኩ ተጠቅመውበታል። የመሰረት ደንጋዩን ያስቀመጡላቸው ግን እነፍቅረስላሴ ናቸው። ወያኔ አገርን በመበተን ከደርግ የከፋ ቢሆንም የደርግን ዘመን የሚናፍቁ ካሉ የዚያ ስርዓት ተዋናዮችና ተጠቃሚዎች የነበሩ ብቻ ናቸው። የኢትዮጵያ ህዝብ ከሁለቱም አምባገነኖች የተሻለ ዴሞክራሲያዊ ስርዓት ይገባዋል።

ወደ ተነሳሁበት የእስር ጉዳይ ልመለስና በደርግ ሆነ በወያኔ መታሰርን በተደጋጋሚ ቀምሼዋለሁ። ለምን ታሰርሁ ብዬ አልቆጭም። ከህዝቡ መከራ የተጋራሁበት እውነተኛ የህይወቴ ምዕራፍ ስለነበር ባሰብሁት ቁጥር መጠነኛ የመንፈስ እርካታ ይሰማኛል። ሁለቱም ስርዓቶች በጣም ፈሪዎች ስለሆኑ በጣም ጨካኞች ናቸው። የተማሩትንና ለስልጣን ተቀናቃኝ ይሆናሉ ያሉትን ማሰርና በግፍ መግደላቸው እንዳለ ሆኖ በሁለቱም ስርዓቶች የሰባና የሰማንያ ዓመት በጤና የደከሙ ከፊሎችም ዐይናቸው የታወሩ አዛውንቶች ያለፍርድ እስር ቤት ቀስ እያሉ በሞት ሲያሸልቡ አይቻለሁ። መደገፍያ ከዘራቸውን ማንሳት የማይችሉትን አዛውንትና ክፉና ደግ የማያውቁ ህፃናትን የስርዓታቸው ተቀናቃኝ አድርገው የሚባንኑ አምባገነኖች ናቸው ሁለቱም።

ያ ሁሉ መጨፍጨፍ፣ ያ ሁሉ እስር የደርግን ስርዓት ከመፈራረስ፣ መንግስቱን ከመፈርጠጥ፣ ጓደኞቹን እነፍቅረስላሴንና ለገሰን እንደበግ ከመጎተት አላዳናቸውም። የጊዜ ጉዳይ ነው እንጂ ወያኔዎች ግድያውን፣ እስሩን ካስተማራቸው ከደርግ በባሰ ሰልጥነው ውድቀቱንም እየወረሱት ነው። የተፈጥሮአቸው እድገት ጣርያ (ክላይማክስ)ላይ ደርሰው ቁልቁለቱን ጀምረዋል። የገነቡት ሁሉ እየተናደ እንዳይቀብራቸው ራስን የማዳን ጥድፊያ ላይ ተጠምደዋል። ይህ መንፈራገጥ ግን የበለጠ ሚዛናቸውን እያሳታቸው ቁልቁል ይወረውራቸዋል። ሲወድቁ በሚያደርጉት መንፈራገጥ ብዙ ጉዳት ማድረሳቸው ግን የተጠበቀ ነው። የወያኔ የአጥቂነት ጊዜ አልፎበት አሁን በመከላከል ላይ ተጠምዷል። ጅኒው ከጠርሙሱ ወጥቷልና መልሶ የመክተት አስማት የሚሠራ አልሆነም።

ታላቁ ሩስያዊ ደራሲ፣ የታሪክ ምሁርና የሶብየትን አምባገነንነት አጥብቆ ይተች የነበረው አሌክሳንደር ኢሳየቪች ሶልዝሄንጺን የሩሲያውያንን መከራ ለዓለም በሚገባ ካሳወቀባቸው በርካታ ሥራዎቹ ዘ ጉላግ አርፒላጎ የዘረዘራቸውን ስናነብ ደርግና ወያኔዎች ያንን እያነበቡ የፈጸሙ ይመስለናል። በአንደኛው ጽሁፉ  “እኛ በሚሊዪን የንምቆጠር ሩስያውያን ሴቶችና ወንዶች ከቀን ቀን፣ ከዓመት ዓመት ራሳችንን ደፍተን ወደ እስር የምንጎተትበት ምክንያት ይህ ነው። የማስጠንቀቂያ ደወል አናጮህም። በጎዳናዎች ተቃውሟችንን አናሰማም። እንዲያውም በተቃራኒው በጎዳና ላይ በጓደኞቻችን ፊት ስንነዳ እኛ ግዞተኞች ምንም እንዳልተፈጸመብን ፊታችንን ቅጭም አድርገን አንገታችንን ደፍተን፤ እነሱ የነገ ግዞተኞችም እኛን እንዳያዩ ዐይናቸውን መሬት ላይ ተክለው እንተላለፋለን። ህዝባችን ይህንን ድርጊት ሂደቱን ሳያዛባ ተግባራዊ ማድረጉን ተክኖበታል። በብዙ ማሰቃየት የታጀበው ምርመራ ሲጠናቀቅ እኛ ትንንሾቹ አሳዎች መረባቸው ውስጥ ዋኝተን እንገባላቸዋለን። …ባህሩን የሞላን ጥሩ አሳዎች፤ የአጥማጆቻችንን መንጠቆ ጉሮሮአችን ውስጥ ለማስገባት የምንሽቀዳደም፤ እኛን በመጎተት እንዳይደክሙ  ወደ ላይ ቀዝፈን የምንቀርብላቸው…..” እያለ ለአምባገነኖች የመከራ ማገዶነት ምንም ሳይንፈራገጡ ወደ ማረጃው፣ ወደ እስሩ የሚሽቀዳደሙ ሩሲያውያንን የሸነቆጠበት አነጋገር እኔንም እንዳለንጋ መንፈሴን ይተለትለዋል።

በአሁኑ ሰዓት በመደበኛ እስር ቤቶች፣ በጦር ካምፖችና በድብቅ እስር ቤቶች የሚማቅቀውን ኢትዮጵያዊ ቁጥር ማወቅ ይከብዳል። በደፈናው እኛና ዓለም የሚያውቃቸው ደፋርና ለዴሞክራሲ ስርዓት ማበብ ከፍተኛ መስዋዕት በመክፈል ላይ ያሉትን አንዱዓለም አራጌ፣ እስክንድር ነጋ፣ ርዕዮት ዓለሙ፣ ውብሸት ታዬ፣ በቀለ ገርባ፣  አቡበከርና ጓደኞቹ ……እያልን ብንዘረዝር ቁጥራቸው የትየለሌ ነው።

እነዚህ ከላይ የጠቀስኳቸው በአካል የተገደቡ እስረኞች ናቸው ብንልም በመንፈስ ልዕልና ያላቸው ንፁሃን ናቸው። በእኔ አስተያየት እነሱ ሳይሆኑ እኛ ቀሪው ኢትዮጵያውያን ነን እስረኞች እላለሁ። እስክንድር፣ አቡበከር፣ ውብሸት፣ ርዕዮትና አንዱዓለም በአካል ከታሰሩበት ወህኒ ዘልቀው በመንፈስ ነጻ መሆናቸውን አሳውቀውናል። ያሉበትን መከራ እንደ ኢምንት በመቁጠር የምንከፍለው ቀላል ነው እያሉ ምንም ለመክፈል ያልተዘጋጀነውን፣ ከዳር ቆመን በፍርሃት የምንርደውን ህሊናችን እንዲሞግተን በመተው ባለ እዳ አድርገውናል።

ርዕዮት፡ “በኢትዮጵያ ፍትህ ማጣትና ጭቆና የተንሰራፋ በመሆኑ ለህይወቴ አዳጋ ይኑረውም አይኑረው ለእውነት እቆማለሁ” ብላለች። ይብላኝ ለእኔና ለእናንተ ዳር ለቆምነው።

አንዱዓለም፡ “ያልተሄደበት መንገድ” በሚል ርዕስ ከእስር ቤት ጠባብ ክፍል በጻፈው መጽሃፉ “እስር የስቃይ ብቻ ቢሆንም ከነፃነትና ከዴሞክራሲ እጦት አይከብድምና በጸጋ መቀመል ነበረብኝ”  ሲል የአካል ስቃይን ፈርተን ህሊናችንን ለአሰርነው አማራጩን ይነግረናል። ከዚያም አልፎ “ይህ ሁሉ የመከራ ሸክም የማን ነው? የታሳሪ ፖለቲከኞች ብቻ ወይስ የነፃነት ናፋቂ ኢትዮጵያውያን ሁሉ?”  በማለት የፍትህና የነፃነት ናፍቆታችን አፋዊ በመሆኑ ህሊናችን እንዲወቅሰን ጥያቄውን ወረወረልን።

እስክንድር፡ ሰሞኑል ለልጁ (ርዕሱ ለልጁ ይሁን እንጂ መልዕክቱ ለእኛ ነው) ከእስር ቤት በፃፈው ደብዳቤ “በጣም ናፍቄሃለሁ። እናትህንም ጭምር። ስቃዩ አካላዊ ስቃይ ብቻ ነው የሚሆነው። የቤተሰባችን ስቃይ ለረጂም ጊዜ መከራ ከተሸከመው ህዝባችን ተስፋ ጋር የተቆራኘ ነው።ከዚህ የበለጠ ክብርም የለም።ስቃዩን ሁሉ በመቋቋም፣ የሚቻለውን ሁሉ ርቀት በመሄድ፣ማንኛውንም አቀበት በመውጣት፣የትኛውንም ባህር በማቋረጥ ነፃነት ላይ በመድረስ ጉዞአችንን ማጠናቀቅ አለብን። ከዚህ ያነሰ ትግል ህሊናን ማደህየት (ባዶ ማስቀረት)ነው” ሲል ጽናቱንና የምንሄድበትን እርቀት አመልክቶን “አምባገነንነት ፍርሃት የነገሠበት በመሆኑ መንግስታዊ ሽብር፣ እስራትና ማሰቃየት ዋነኛ ተግባሩ ነው። በዚህ መንገድ ግን ሁሉንም ህዝብ ማንበርከክ አይቻልም። ነገር ግን የተወሰኑ ሰዎችን የጥቃት ኢላማ በማድረግ ብዙውን ሰው በፍርሃት ማደንዘዝ ይችላሉ። በጥቁር ዓለም ጥንታዊ የመሆናችን የጋራ ኩራት ይህንን አስማት ለመጨረሻ ጊዜ እንድንሰብረው ያስገድደናል” ሲል በነሱ መታሰርና መሰቃየት ሩቅ ሆነን በፍርሃት ተሸብበን የታሰርነውን ሊፈታን ይታገላል።

ሌሎችም እስረኞች ደጋግመው በተለያዬ መልክ ያስተላለፉልን መልዕክት ይሄው ነው። ኢትዮጵያ ውስጥ ያለው ህዝብ በአጠቃላይ እስረኛ መሆኑ ቢታወቅም ውጭ ያለነው እንኳ በፍርሃት፣ በራስ ወዳድነት፣ በክፍፍል፣ በመከነና የትም ባላደረሰን የትናንት አስተሳሰብና ከዚያም አልፎ በስሜታዊነት እስረኛ ነን። አንዱዓለም፣ እስክንድርና ሌሎችም የሚሉን ‘አሳሪ ሳይኖራችሁ ራሳችሁን ያሰራችሁ ራሳችሁን ነፃ አውጡና ትልቅ አገራዊ ዓላማ ይዘን አገር ነፃ እናውጣ’ ነው የሚሉን።

የጽሁፌ ማጠቃለያው ሁላችንም እስረኞች ነን።በመጀመርያ ራሳችንን ነፃ እናውጣ። ከዚያ የታሰሩ ወንድሞቻችንን፣ እህቶቻችንንና አገራችንን ነፃ ማውጣት እንችላለን።

ግለሰብ ሆኖ በህሊናው፣ ድርጅት ሆኖ በአሰራሩ ነፃነት ከሌለው ለነፃነት ቆሜያለሁ ማለት ከአፋዊነት አይዘልም። እስከ አሁንም የሆነውና ያየነው ይህንኑ ነው። ራሳችን ለራሳችን የነፈግነውን ነፃነት ከአምባገነኖች በልመና አናገኝም።

ኢትዮጵያን እግዚአብሄር ይባርክ!

ጸሃፊውን በamerid2000@gmail.com ማግኘት ይቻላል

↧

የኢትዮጵያ ሙስሊሞች በአዲስ አበባ እና በክልል ከተሞች ያካሄዱት ደማቅ የተቃውሞ ትእይንት ቪድዮዎችን ይዘናል

$
0
0

በአዲስ አበባ እና በክልል ከተሞች ደማቅ የተቃውሞ ትእይንት ተደረገ (ቪድዮዎች ይዘናል)
በአዲስ አበባ ታላቁ አንዋር መስኪድን ጨምሮ በተለያዩ የሃገሪቱ ዋናዋና ከተሞች ‹‹ሰላታችንን በመስጂዳችን!›› በሚል መሪ ቃል ህዝበ ሙስሊሙ እያካሄደው ያለው መስጂድ ተኮር የዘመቻ እንቅስቃሴ አካል የሆነው እና የዘመቻው ማጠናቀቂያ የጁምኣ የተቃውሞ ትእይንት በደመቀ መልኩ ተካሂዷል::

ህዝቡን ከመስጂዱ ለመነጠል በመንግስት በኩል እየተሰራ ያለውን ህገ ወጥና ኢ-ህገ መንግስታዊ ስራም ለራሱ ተረድቶ ላልሰሙት ሁሉ በማሰማትና መስጂዶቹን በዒባዳ በማድመቅ ላይ ነው የሚገኘው፡፡ ይህ ወቅታዊና አንገብጋቢ የመስጂድ ባለቤትነትን የማረጋገጥ እንቅስቃሴ የመንግስትን እና የመጅሊስን ሴረኞች እንቅልፍ ማሳጣቱንም ከተለያዩ አቅጣጫዎች የሚመጡ የውስጥ መረጃዎች እያጋለጡ ነው፡፡ ‹‹ሰላታችንን በመስጂዳችን!››ዘመቻ የዛሬው ጁሙአ ድረስ ቀጥሎ የቆየ ሲሆን በአዲስ አበባና በተመረጡ የክልል መስጂዶች ላይም አስቀድሞ የነበሩንን ቋሚ ትዝታ ጥለው ያለፉ ግዙፍ ተቃውሞዎችን በሚያስታውስ መልኩ የደመቀ የተቃውሞ ስነስርአት በማድረግ በሰላማዊ ሁኔታ ዘመቻው መጠናቀቁ ታውቋል::

በዚህም መሰረት ከቀኑ ስድሰት ጀምሮ በአዲስ ወደ አዲስ አበባ አንዋር መስኪድ እና በተለያዩ ከተሞች በሚገኙ የተቃውሞ ወደተመረጡ መስኪዶች የተመመው ህዝበ ሙስሊሙ የመስኪዶችን ውስጥ እና ደጅ በመሙላት መስኪዶቹ የራሱ ሃብት መሆናቸውን እና ሙስሊሙ ህዝብ ሰላም ፈላጊ መሆኑን በደመቀ ተቃውሞ ነጭ ምልክቶችን በማውለብለብ ገልጿል::

ህዝበ ሙስሊሙ ዘመቻውን በተሳካ መልኩ በማድረግ ሰላማዊ ተቃውሞውን አሰምቶ ከኮሚቴው ጎን ዛሬም ቃሉን አክብሮ እንደቆመ በማሳየት በሰላም መመለሱን ለማረጋገጥ ተችሏል::

↧

[የሳዑዲ ጉዳይ] ዲፕሎማቱ የኢትዮጵያ አለም አቀፍ ት/ቤትን ተቆጣጠሩ፤ ለተመዘበረው 1.7 ሚሊዮን ሪያል «ከ6 ሚሊዮን ብር በላይ» ወላጆችን ባለዕዳ አደረጉ

$
0
0

saudi arabia
ከኢትዮጵያ ሃገሬ ከሳዑዲ አረቢያ ጂዳ

ከ1500 በላይ በሆኑ ወላጆች በባለቤትነት እንደሚተዳደር የሚታወቀው በሪያድ አለም አቀፍ የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ ት/ቤት በዲፕሎማቱ ቁጥጠር ስር መዋሉን የሚገልጹ ምንጮች ለዛሬ ማርች 28 2014 በኤምባሲው ደብዳቤ የስብሰባ ጥሪ ተላልፎላቸው የነበሩ ወላጆች ባለመገኝታቸው የስብሰባው አዳራሽ ባዶ ሁኖ መዋሉን አክለው ገልጸዋል፡:

ንበረትነቱ በሪያድ የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ ማህበር እንደነበር የሚነገርለትን ት/ቤት ኤምባሲው ለመቆጣጠር እያደረገ ያለው ጥረት ከግልጥቀም የመነጨ መሆኑንን የሚናገሩ ውስጥ አውቂ ምንጮች ት/ቤቱን ከኮሚኒቲው በመነጠል ከወላጆች በሚመረጥ የቦርድ አስተዳደር ይመራል በሚል ሽፋን ላለፉት 5 አመታት በት/ቤቱ ጥሬ ገዝንዘብ ላይ ግልጽ የሆነ ምዝበራ መፈጸሙን ይናገራሉ። ይህን አለም አቀፍ የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ ት/ቤት ዲፕሎማቱ ልግል ጥቅማቸው ለማዋል ያልፈነቀሉት ድንጋይ ያልበጠሱት ቀጠል እንደሌለ የሚናገሩ ወገኖች ከዛሬ 7 ወር በፊት ለይስሙላ ህብረተሰቡ በቦርድ አባልነት ለመሳተፍ የሚያስችለውን ማስታወቂያ አውጥተን የሚቀርብ ሰው አጣን ለማለት የመወዳደሪያውን ማመዘኛ ዲግሪ እና ከዛ በላይ ከፍ በማድረግ ማንኛውም ወላጅ በቀላሉ ማቀረብ የማይችላችውን ተጨማሪ ድብዳቤዎች እንዲያቀርብ የሚጠይቅ መስፈርቶችን በማስቀመጥ ወላጆች ት/ቤታቸውን ለማስተዳደር እንዳይችሉ መደረጋቸውን ይገልጻሉ።

ይህ በዚህ እንዳለ ወላጆች ባላቸው አቀም እና የትምህርት ደረጃ አቋቁመው ለዘመናት ያለማንም ድጋፍ እና ረዳት በማስተዳደር ለዚህ ያበቁትን የልጆቻቸውን ዕውቀት መገብያ ማዕከል ኤምባሲው ለመንጠቅ በሪያድ የዲያስፖራው ሃላፊ እንደሆኑ የሚነገርላቸው አቶ ተመስገን ኡመርን በጓሮ በር አሾልኮ በመስገባት ቀደም ብለው ያዘጋጇቸውን ታማኝ አገልጋይ የቦርድ አባላት ስልጣን ካፀደቁ በሃላ ዛሬ ወላጆችን ለማደናገር በኤምባሲው ማህተም በተደገፈ ደብዳቤ ስብሰባ መጥራታቸው የዲፕሎማቱን አላውቂ ሳሚነት በግልጽ ያሳይል ተብሏል።

ዲፕሎማቱ በኤንባሲ ሽፋን ህገወጥ ተግባር በመፈጸም ላይ እንደሚገኙ የሚናገሩ ወገኖች 1500 በላይ የሆኑ ወላጆች በባለቤትነት እንደሚቆረቆሩለት የሚነገርለትን ት/ቤት ቁጥራቸው ከ 50 የማይበልጥ የት/ቤቱ ጉዳይ የማይመለክታቸውን ደጋፊዎቻቸውን ሰብስበው አዳራሽ በማስገባት «አይጥ በበላው ዳዎ እንዲሉ » ምንም የማያውቁትን ወላጆች የ 1.7 ሚሊዮን ሪያል ባለእዳ የሚያደርግ ሪፖርት በዲይስፖራው ሃላፊ አማካኝነት በማቅረብ ዲፕሎማቱ የመረጣቸውን ህገ ወጥ የቦርድ አማራር አባላት ህጋዊ ለማድረግ ከወላጆች ጀርባ ዛሬ የፈጸሙት ደባ በህግ ሊያስጠይቃቸው የሚገባ ብሄራዊ ወንጀል መሆኑን ገልጸዋል። ስብሰባው ላይ በሳውዲ አረቢያ የኢትዮጵያው አምባሳደር ዶ/ር መሃመድ ህሰን መገኘታቸውን ለማረጋገጥ ተችሏል። በዚህ ዙሪያ የዲያስፖራውን ሃላፊ አቶ ተመስገን ዑመርን ለማነጋገር ያደርኩት ሙከራ አልተሳካም::

↧
↧

ዘ-ሐበሻ ጋዜጣ ቁጥር 61 – PDF

$
0
0

ጋዜጣውን ለማንበብ እዚህ ይጫኑ

ዘ-ሐበሻ ጋዜጣ ቁጥር 61 ወጥታለች። በሚኒሶታ የምትኖሩ ከ92 በላይ ቦታዎች ላይ ጋዜጣችን ስለተቀመጠ ማግኘት ትችላላችሁ። በውጭ ያላችሁ ደግሞ በPDF አቅርበንላችኋል።

zehabesha 61 page page 13 to 24
* ከሚኒሶታ አልፎ በዓለም አቀፍ ደረጃ መነጋገሪያ እየሆነ የመጣው የሚኒሶታው ደብረሰላም መድሃኔዓለም ቤ/ክ ጉዳይ ዓብይ ር ዕሳችን ነው። ጉዳዩ ወደ ወሳኝ ምዕራፍ ተሸጋግሯል፤ ብዙሃን በጉጉት ሲጠበቁት የነበረው ጠቅላላ ጉባኤም ተጠርቷል።

* የተመስገን ደሳለኝ አዲስ ጽሁፍ “ኑ እንዋቀስ! ኢሕ አዴግን እናፍርሰው” የጋዜጣችን አካል ሆኗል

* የኦሮሚያ ክልል ፕሬዚዳንት የነበሩት አቶ አለማየሁ አቶምሳ እንዴት በምግብ መመረዝ ሊሞቱ ይችላሉ? – አንድ የህክምና ባለሙያ በምግብ መመረዝ የተነሳ የሚከሰቱ 4 በሽታዎችን ይዘውልናል – ያንብቡት።

* በቀድሞው ጦቢያ መጽሔት ላይ ተወዳጅ ብ ዕሩን የምታነቡለት ጸጋዬ ገብረመድህን አረአያ “የመስዋዕትነት ወንጌል” የሚል ጠንካራ ዘገባ አድርሶናል – ያንብቡት።

በእንመካከር አምዳችን፡ 3 ጉዳዮች ተይዘዋል።

* “ፍቅረኛዬ በወሲብ ወቅት ተቃጠልኩ፤ አሳመምከኝ እያለች አስቸገረችኝ”
* ትዳር የሚመሰርቱት ምን ዓይነት ፍቅረኞች ናቸው?
* ሰዎች “ውስጣዊ ውበት እወዳለሁ” ሲሉ እሰማለሁ ምንድ ነው? ለሚሉት የባለሙያ ምላሾችን ይዘናል።

በአሜሪካ ጉዳይ አምዳችን፦
* ቤትዎ ከመሸጡ በፊት ከመንግስት በሚያገኙት ዕርዳታ ማትረፍ ይችላሉ ይለናል የጠበቃ ሳምሶን በዙ ጽሁፍ። ቢያነቡት ይጠቀማሉ።
* በሰሜን አሜሪካ ሁካ (ሺሻ) በጣም እየተለመደ የመጣ ነገር ሆኗል። ለመሆኑ ሁካ ምን ይጠቅማል? ምን ይጎዳል? የሚል አስተማሪ ዘገባ ይዘናል። ለጤናዎ የሚያስቡ ከሆነ ያንብቡት።

እንደተለመደው በጤና አምዳችን 3 ጉዳዮችን ይዘንላችኋል።
* ምን ልብላ? What Should I Eat?
* የማደንዘዣ ቴክኒክ ምስጢር፤ ከህሊናችን ስንርቅ የት እንገባለን?
* ኢንዶስኮፒ ለማን እና ለምን? – ያንብቧቸው።

ለእረፍትዎ አምዳችን ላይ 2 ጉዳዮች ተይዘዋል።
* የጆሮ፣ አፍንጫና ጉሮሮ አስገራሚ ወዳጅነት
* ሰዎች ከእንስሳ ሊለዩ የሚችሉባቸው 15ቱ ልዩ ዘዴዎች

በስፖርት አምዳችንም 3 ጉዳዮች ተስተናግደዋል።

* የዓለም ዋንጫ እየተቃረበ ቢሆንም የጀርመን አቋም አሳሳቢ ሆኗል፤
* ስለማን.ሲቲ፣ባርሴሎና እና እንግሊዝ ዣቪ ይናገራል
* ቲያጎ የባርሴሎናው ዣቪ አልጋ ወራሽ – ይዝናኑባቸው።

በሴቶች ጤና አምዳችን ሴቶችን በብዛት ስለሚያጠቃው የኩላሊት ኢንፌክሽን ላይ ጥሩ ዘገባ አቅርበናል።

ምን ይሄ ብቻ?
የዲ/ን ዳንኤል ክብረት፣ የኤፍሬም እሸቴ፣ የዶ/ር ፍቅሬ ቶለሳን ጨምሮ ሌሎች አዝናኝና አስተማሪ ዘገባዎችን ከማስታወቂያዎች ጋር አጅበን ይዘናል። ያንብቡን።

↧

አርቲስት ግሩም ኤርሚያስ የጥፋት ሐዋርያ ሲሆን

$
0
0

(ከአሌክስ አብርሃም)
ዛሬ ማታ ማለትም በ 20 /07/ 2006 ዓ/ም በሰይፉ ፋንታሁን እየተዘጋጀ በኢቢኤስ ቴሌቪዥን በሚተላለፈው ሾው ላይ የተመለከትኩት አሳፋሪ ድርጊት ይህን እንድፅፍ አነሳስቶኛል !
የሰይፉ እንግዶች አርቲስት አለማየሁ ታደሰ ፣ አርቲስት ግሩም ኤርሚያስና ኮሜዲያን ደረጀ ሃይሌ ነበሩ … (በዚህ አጋጣሚ ሶስቱንም እስከዚህ ጊዜ ድረስ የማከብራቸውና የማደንቃቸው አርቲስቶች መሆናቸውን እወቁልኝ ) እናም ሰይፉ ስለስራቸው ስለግል ሂወታቸው እየጠየቃቸው ውይይቱ ሞቅ ብሏል … (ወደ 33ኛው ደቂቃ አሳልፈው ያዳምጡት)

በመሃል ሰይፉ ቀለል አድርጎ አንድ ጥያቄ ለአርቲስት ግሩም ኤርሚያስ አቀረበ

‹‹ በቀረፃ ላይ ላለ ፊልም የአንድ ‹ድራግ› ተጠቃሚን ወጣት ገፀ – ባህሪ ተላብሰህ ስትጫወት ድራግ ወስደህ ነበር ይባላል ..እውነት ውሸት ?
ሚሊየን ኢትዮያዊያን ወጣቶች ታዳጊወችና ህፃናት የሚያውቁት አርቲስት ግሩም ሚሊየኖች በሚመለከቱት ፕሮግራም ላይ እንዲህ ሲል መለሰ
‹‹እውነት !! ››
Girum Ermias‹‹እንዴት ነበር አጋጣሚው ምንስ ተሰማህ›› ሰይፉ ጠየቀ
‹‹ በትወና ላይ ማስመሰል ሳይሆን ሁኖ መስራት የሚባል ነገር አለ… መምህሬ አለማየሁ ሊረዳኝ ይችላል (አለማየሁ በመስማማት ራሱን ነቀነቀ ) እናም በጭስ ተከልየ (?) የሚል ፊልም እየሰራን ነው … ቀረፃው ላይ የወከልኩትን ገፀ ባህሪ ወክየ ሳይሆን ‹ ሁኘ › ለመስራት ሃሽሽ (ድራግ) ወሰድኩ ..በቃ ጉልበቴ ተንቀጠቀጠ ዞረብኝ …..›› ሲል ሰፊ ማብራሪያ ሰጠ …

ይህን ፀያፍ ድርጊት እንደትልቅ የጥበብ ክስተት ማውራቱ ሳያንስ ጭራሽ በሃሽሽ ደንዝዞ መናገር ሁሉ አቅቶት ቀረፃ ላይ ባጋጣሚ የተወሰደውን ምስል በመሃል አስገብተው ያሳዩት ጀመረ … ይህ አሳፋሪ ቪዲዮ ታይቶ ሲያበቃ በአዳራሹ የታደመው ሰው ሞቅ ያለ ጭብጨባ ‹በሃሽሽ ደንዝዞ› ለታየው ‹‹አርቲስት ›› ለገሰ …..ሰይፉን ጨምሮ ! አለማየሁ ታደሰና ደረጀ ሃይሌን ጨምሮ !

1ኛ . በኢትዮጲያ ወንጀለኛ መቅጫ ህግ (ኧረ በብዙ የአለማችን አገራት ጭምር) አደንዛዥ እፆችን መውሰድም ይሁን በማንኛውም መንገድ ማቀባበል ይዞ መገኘት ቁልጭ ብሎ የተቀመጠ ወንጀል እንደሆነ ሰምተናል ( በማንኛውም ሁኔታ ቢሆን ) ይህን ፀያፍ ድርጊት አደባባይ አውጥቶ በትወናም ይሁን በሌላ ተልካሻ ምክንያት በሚሊየን ለሚቆጠሩ ወጣቶች ማሳየት ምናይነት ሃላፊነት አለመሰማትና ስርአት አልበኝነት ነው ?
2ኛ . አንድ ትልቅ እውቅና ያለው አርቲስት በርካታ ኢትዮጲያዊያን ተመልካቾች ባሉት ሾው ላይ በሃሽሽ ደንዝዞ ሲቀባጥር የሚታይበትን ቪዲዮ ማሳየት (ያውም እንደታላቅ ክብር በጭብጨባ ታጅቦ )የብሮድካስት ባለስልጣን መስሪያቤት …የኢቢኤስ ቴሌቪዥን አስተዳዳሪወች እንዲሁም የሾው ባለቤት ሰይፉ ፋንታሁንን የሚያስወቅስ (ጠያቂ ቢኖር በህግም የሚያስጠይቅ) ፀያፍ ተግባር ነው ! ምስሉን ካሳዩ በኋላ ‹‹ድራግ አይጠቅምም ጎጅ ነው ምናምን እያሉ ማውራቱም ቢሆን ከድርጊቱ በላይ ተፅእኖ የሚያሳድር ምክር አይደለም ) እዚች አገር ላይ ለትውልድ የሚገደው ማነው …የሚዲያወቻችን ስርአት አልበኝነትስ ሃይ የሚባለው በምን መንገድ ይሆን ?
3ኛ. በትወና ሰበብ ስክርቢቱ ላይ ድራግ መውሰድ ስለተፃፈ ስሜቱን ለመሞከር እና ‹‹መስሎ ሳይሆን ሁኖ›› ለመስራት ይህን ማድረጉ እንደአንድ የጥበብ መንገድ ከተወሰደ ( መምህሩ አለማየሁ ታደሰም ስላረጋገጠ) ወሲብ ነክ ስክርቢቶች ላይም ወሲብ መፈፀም ሙያዊ ፈቃድ ሁኖ ሊታይ ነው ማለት ነው ?

በዚህ አይነት አገራችን ላይ ከስር እንደአሸን የሚፈላው ፊልም ሰሪ ወጣት ሁሉ ‹‹መስሎ ሳይሆን ሁኖ›› ለመስራት በሚል ሰበብ ‹‹ወደ ፊልም ኢንዳስትሪ›› ሳይሆን ‹‹ወደብልግና ኢንዳስትሪ›› እንዲጎርፍ አንጋፋወቹ መንገድ እየከፈቱለት መሆኑን መታዘብ ይቻላል (አውቀውም ይሁን ሳያውቁ )
በአጠቃላይ ይህን ፀያፍ ድርጊት ለፈፀመው ግለሰብ …ምስሉን እንደደህና ነገር በጭብጨባ አሳጅቦ ላቀረበው የዝግጅቱ ባለቤት እንዲሁም ለህዝብ እንዲደርስ ላደረገው የቴሌቪዥን ጣቢያ ድርጊቱ ከእናተ የማይጠበቅ እጅግ የወረደና በ ሱስ አፋፍ ላይ የቆመውን በርካታ ወጣት ወደሱስ አዘቅት የሚገፋ ድርጊት መሆኑን መዘንጋት የለባችሁም እላለሁ !

ከፍ ያለ አደራ የተጣለበት የጥበብ ሰው እንኳን በአደባባይ በጓዳውም ቢሆን ትውልድን የሚያንፅ ወደበጎ ነገር የሚመራ ድርጊት ይፈፅም ዘንድ የሙያው ድስፕሊን በራሱ ያስገድደዋል ! መንግስትም ይሁን የሚመለከተው አካል ይህን ጉዳይ ዝም ቢልም በበኩሌ ይህን የአርቲስቱን ድርጊት በፅኑ እቃወመዋለሁ ! አጥፊና ፀያፍ ድርጊት ነው ግሩም ኤርሚያስ አዝናለሁ !!

↧

ኢህአዴግን የምደግፍበት አንድ ነገር አገኘሁ- መሬት አይሸጥም አይለወጥም! –ፋሲል የኔዓለም (ጋዜጠኛ)

$
0
0

ጋዜጠኛ ፋሲል የኔዓለም

ጋዜጠኛ ፋሲል የኔዓለም

ለመጀመሪያ ጊዜ ኢህአደግን የምደግፍበት ነገር አግኝቻለሁ። ኢህአዴግ በመቃብሬ ላይ ካልሆነ መሬት አይሸጥም አይለወጥም ይላል። ትክክለኛና ብራቮ የሚያስብል አቋም ነው።
መሬት የሃብት ሁሉ ምንጭ ነው፤ መሬት ያለው “ምንም” ነገር ባይኖረው ሃብታም ነው። ከጊዜ በሁዋላ እንኳንስ የእርሻና የቤት መስሪያ ቦታ ማግኘት ቀርቶ ለመቀበሪያ የሚሆን ቦታ ማግኘትም ጭንቅ ይሆናል – የሰው ልጅ እንደ አሜባ በፍጥነት ይራባል፣ መሬት ደግሞ በዛው ልክ እየጠበበች ትሄዳለች። እናም ይህን ብርቀየ ሃብት በስርዓት መንከባከብ ግድ ይላል።

መሬት በግለሰቦች እጅ መሆኑ ምርትን ለማሳደግ ይጠቅማል የሚለው መከራከሪያ አሳማኝ ነው ። ኢህአዴግ ገበሬውንና የከተማውን ሰው እንደፈለገ የሚቆጣጠረው መሬት የመንግስት ስለሆነ ነው የሚለው መከራከሪያም እንዲሁ አሳማኝ ነው። ለመሬቱ ሲል ፈቅዶ የኢህአዴግ ባሪያ ለመሆን የመረጠ ብዙ ወገን አለ፤ መሬትን ነጻ ማድረግ ኢህአዴግ ከዘረጋው የባርነት ቀንበር ነጻ ለመውጣት አንድ እርምጃ ነው ተብሎም ሊታሰብ ይችላል። እርግጠኛ ባልሆንም እያመነታሁ እቀበለዋለሁ። ። በአጭሩ መሬት ወደ ግለሰቦች መዞሩን በመርህ ደረጃ እደግፋለሁ። ነገር ግን ዘረኝነትና ሙሰኝነት ባህሪው በሆነው መንግስት ስር ሆነን፣ መሬት ወደ ግል ይዙር ቢባል ከጥቅሙ ይልቅ ጉዳቱ የሚያመዝን ይመስለኛል ፣ ከኢህዴግ ባርነት ነጻ እንወጣለን ስንል የዘመናት ባርነትን እንዳንከናነብ እሰጋለሁ ። ኢህአዴግ ፍትሃዊ በሆነ መልኩ መሬትን ወደ ግል የማዞር ብቃት የለውም። ይህን ደግሞ በ1980ዎቹ፣ በአማራ ክልል የመሬት ክፍፍል በተደረገበት ወቅት አይተነዋል። ሰዎች በፖለቲካ አቋማቸው ብቻ መሬት እንዳያገኙ መደረጉን በጊዜው ይወጡ የነበሩትን ዘገባዎች አይቶ ማረጋገጥ ይቻላል።
አዲስ ስርአት እስኪመጣ መሬት ወደ ግል ባይዞር በብዙ መልኩ ተመራጭ ነው።
Omo River
ባለፉት 23 ዓመታት ዋና ዋና የሚባሉ የከተማ መሬቶችን የህወሃት ሹሞችና ተላላኪዎቻቸው ተቆጣጥረዋቸዋል። ከከተሞች አልፎ በገጠር ለም የሚባሉትን የእርሻ መሬቶችንም እየተቆጣጠሩዋቸው ነው። ጋምቤላ፣ ኦሮምያ፣ ቤንሻንጉል፣ አፋር እንዲሁም ሰሜን አማራ ብትሄዱ ሰፋፊ መሬቶች በዘመኑ ሰዎች የተያዙ ናቸው። በአዲስ አበባ በአንድ ወቅት በተደረገ ጥናት አብዛኞቹ የከተማዋ ቁልፍ መሬቶች በህወሃትና ተላላኪዎቻቸው የተያዙ መሆኑ ተረጋግጧል ። መሬትን እየተሽቀዳደሙ የመያዙ እሩጫም በቀላሉ የሚቆም አይመስልም፣ አይቆምም። በሚቀጥሉት 5 ዓመታት ( ኢህአዴግ በህይወት ከኖረ) እስካሁን ያልተያዙት ሰፋፊ የእርሻና የከተማ ቦታዎች በጥቂት የዘመኑ ባለሃብቶች ቁጥጥር ስር እንደሚውሉ ለመተንበይ ሼህ ጅብሪል ወይም የፍጥሞውን ዮሃንስ መሆንን አይጠይቅም። ምክንያቱም ግልጽ ነውና ። መሬት የሃብት ምንጭ ነው፤ ሃብት ያለው ጉልበት አለው፤ ጉልበት ያለው ስልጣን አለው፤ ስልጣን ያለው ሁሉም አለው ።

አሁን ባለው መንግስት መሬት ወደ ግል ይዞታ ይዙር ማለት ላለፉት 22 ዓመታት ሰፋፊ መሬቶችን ዘርፈው የያዙ የዘመኑ ባለሃብቶች የግል መሬት እንዲኖራቸው መፍቀድ ማለት ነው። የሚመጣው መንግስት የእነዚህን ባለሃብቶች መሬት ቀምቶ ለማከፋፈል ቢሞክር ከአለማቀፍ ድርጅቶች ሳይቀር ከፍተኛ ተቃውሞ ይገጥመዋል። በደርግ ዘመን የግል ባለሀብቶች ንብረት ወደ መንግስት በዞረበት ወቅት ከምእራባዊያን አገራት ትልቅ ተቃውሞ መነሳቱን አንዘነጋም። አሁን ባለው የአለም ስርአት የግል ባለሀብቶችን መንካት ማለት ከምእራባዊያንና ከገንዘብ ተቋሞቻቸው ጋር መላተም ማለት ነው። ይሄ መንግስት እስከሚለወጥ መሬት በመንግስት እጅ ከቆየ፣ መጪው መንግስት የእነዚህን ሰዎች መሬት ቀምቶ ለማከፋፈል ቢሞክር ከየትኛውም ወገን ተቃውሞ አይደርስበትም፣ ምክንያቱም መሬት የመንግስት ነውና። ” አስፈላጊው ካሳ ተሰጥቷቸው መሬታቸው ቢቀማ ተቃውሞ አይኖርም ” ቢባል እንኳ፣ በህገወጥ መንገድ ለያዙት መሬት ካሳ መክፈል የሞራልና የፍትሃዊነት ጥያቄ ያስነሳል። አዲሱ መንግስት የኢትዮጵያን የመሬት ስሪት በደንብ አጥንቶና ሁኔታዎችን ሁሉ አመቻችቶ መሬት ወደ ግል ቢያዞር ያን ጊዜ ቁጥር አንድ ደጋፊ እሆናለሁ። ዝምባብዌ ነጻ ከመውጣቱ በፊት መሬት የመንግስት ቢሆን ኖሮ፣ ነጻ በወጣ ማግስት መሬት ከግለሰቦች እየቀማ ያከፋፈለው የዝምባቡዌ መንግስት አሁን የገጠመውን ተቃውሞ ያክል አይገጥመውም ነበር፤ ደቡብ አፍሪካም ነጻ ሲወጣ መሬት የመንግስት ቢሆን ኖሮ፣ የደቡብ አፍሪካ መንግስት ለብዙ ጥቁሮች መሬት እንደፈለገ ለማከፋፈል አይቸግረውም ነበር። በኢህአዴግ ዘመን መሬት ቢከፋፈል የዝምባብዌና የደቡብ አፍሪካ እጣ ይገጥመናል። መሬቱ ሁሉ በጥቂት የዘመኑ ሰዎች እጅ ይገባና እነሱ ” ነጮች” እኛ “ጥቁሮች” እንሆናለን። መጪው መንግስት መሬትን በፍትሃዊነት ማከፋፈል ይችል ዘንድ መሬት በመንግስት እጅ ሆኖ መቆየት አለበት። ኢህአዴግ መውደቁን ካወቀ፣ መሬትን ወደ ግል አዙሮ ለመጪው መንግስት ችግር አውርሶት ያልፍ ይሆን እያልኩ እሰጋለሁ።

በኢህአዴግ ዘመን መሬትን ወደ ግል እንዲዞር መፍቀድ ማለት እነዚህ ጥቂት የዘመኑ ሰዎች አሁን ከያዙትም በላይ ሰፋፊ መሬቶችን በፍጥነት እንዲያግበሰብሱ ሁኔታዎችን ማመቻቸት ማለት ነው። ዘመነኞቹ “መሬት ወደ ግል ሊዞር ነው” የሚለውን ሲሰሙ፣ በውጭ ባንኮች የከዘኑትን ገንዘብ እያወጡ መሬት በፍጥነት ለመግዛት ይጣደፋሉ። ስርአቱም የተወሰኑ ሰዎች ሰፋፊ መሬቶችን እንዲይዙ ሁኔታውን ያመቻችላቸዋል። ያልተያዙ መሬቶችን ለመግዛት ገንዘብ ቢያጥራቸው እንኳን የባንክ ብድር ይመቻችላቸዋል። የመንግስት ድርጅቶች ወደ ግል ሲዞሩ ያየነው ህገወጥ አሰራር በመሬት ሽያጭ ላይ እንደማይደገም ምንም ማረጋገጫ የለም ። የሻኪሶ ወርቅ ማእድን በስንት ነው የተሸጠው? በርካታ የመንግስት የንግድ ድርጅቶች እንዴት ነው ወደ ግለሰቦች የዞሩት? የተሸጡበት ገንዘብ መጠን ለህዝብ ተነግሮ ያውቃል? ገንዘቡስ መንግስት ካዝና መግባቱ ይታወቃል?
ቅንጅት አዲስ አበባን ሲያሸንፍ፣ የስርአቱ ልጆች ሰፋፊ መሬቶችን መቀራመት ጀመሩ፣ ኢህአዴግም ሆን ብሎ ሁኔታዎችን አመቻቸላቸው። ኢትዮጵያ በቅኝ ግዛት ስር ያለች ትመስል ነበር። ቅንጅት ቢጨንቀው ” የመሬት ዝርፊያው በአስቸኳይ እንዲቆም” የሚጠይቅ መግለጫ አወጣ። የሚሰማ ግን አልነበረም። አላሙዲ ሳይቀር ጊዮርጊስ መሃል አደባባይ ላይ ለአመታት አጥሮ ያስቀመጠውን ቦታ እንዳልቀማ ብሎ ለመጀመሪያ ጊዜ አረሰው። ከዚያ ወዲህ ድፍን አስር አመት ምንም ስራ አልሰራበትም። ቅንጅት አዲስ አበባን እንደማይረከብ ሲያውቅ፣ ኢህአዴግ በመናኛ ገንዘብ ያዘረፈውን መሬት መልሶ ለመሰብሰብ ተሳነው። መሬት ወደ ግል ሊዞር ነው ቢባል ተመሳሳይ ነገር እንደሚፈጠር አልጠራጠርም።

በዚህ በዘርና በጥቅም በተማከለ ስርዓት ውስጥ ሆኖ መሬት ወደ ግል ይዙር ብሎ መጠየቅ በራስ ላይ እባብ እንደመጠምጠም ይቆጠራል ። ስለመሬት መሸጥና መለወጥ ለማውራት ኢህአደግ መቃብር እስኪገባ ድረስ መጠበቅ ግድ ይለናል። መታገል ያልብንም ኢህአዴግን ወደ መቃብር ለመሸኘት ነው። በእርሱ መቃብር ላይ አዲስ ስርአት ስንፈጥር ፣ ያን ጊዜ፣ ሁሉንም በማያስደስት ፣ ሁሉንም በማያስከፋ መልኩ መሬት ማከፋፈል ይቻላል።
ኢህአዴግ እስኪወድቅ መሬት በመንግስት እጅ መሆኑን በጽኑ እደግፋለሁ!

( ማሳሰቢያ ይሄ የግል አቋሜ ነው። አንድነት ፓርቲ በቅርቡ
ካስተዋወቀው የሚሊዮኖች ድምጽ ጋር በፍጹም አይያያዝም። ለዚህ ጽሁፍ መነሻ የሆነኝ Wealth Over Work- በሚል ርዕስ ፓውል ክሩግማን The New York Times ላይ የጻፈው ጽሁፍ ነው። በዚህ ዙሪያ ሰፊ ክርክር እንደሚኖር እጠብቃለሁ)

↧

የዓረና መሪዎች በእንደርታ ኲሓ ከተማ በፖሊስ ታሰሩ

$
0
0

አብርሃ ደስታ ከመቀሌ

Arena-Tigray-logoየዓረና አመራር አባላት የሆኑት አቶ ብርሃኑ በርሀ፣ መምህር የማነ ንጉሰና አቶ ፅጋቡ ቆባዕ በፖሊስ ተደበደቡ፤ በመጨረሻም በኲሓ ከተማ ፖሊስ ታሰሩ። የታሰሩበት ምክንያት ለስብሰባ በማይክሮፎን ቀስቅሳችኋል የሚል ነው። ነገ እሁድ በኲሓ ከተማ ማዘጋጃቤት አዳራሽ ስብሰባ ለማድረግ የተፈቀደልን ሲሆን ቅስቀሳ ለማካሄድ ግን ተከልክለናል። ዛሬ ጧት አቶ ዓምዶም ገብረስላሴና መምህር ዮሃንስ ካሕሳይ ቅስቀሳ ሲያደርጉ በዓይናለም ከተማ ለሰዓታት ታስረው ተለቀዋል። የህወሓት ካድሬዎች ዓረና የማዳበርያ ዕዳ እንደሚሰርዝ፣ መሬት የህዝብ እንደሚያደርግ፣ የሊዝ አዋጅ እንደሚያስቀር ወዘተ በማይክሮፎን እንዳይናገር አስጠንቅቁት ተብለናል ሲሉ የህወሓት ካድሬዎች ራሳቸው አረጋግጠውልናል። አሁን የኲሓ ከተማ ቅስቀሳችን በአባሎቻችን መደብደብና መታሰር ምክንያት ለግዜው ቁሟል። ስብሰባው ግን ነገ ይካሄዳል።

ዓረና ፓርቲ ነገ እሁድ ከእንደርታ ህዝብ ጋር በኲሓ ከተማ ለሚያደርገው ህዝባዊ ስብሰባ ቅስቀሳ እንዳያደርግ ተከለከለ። ህወሓቶች ህዝባዊ ስብሰባ እንድናደርግ የፈቀዱልን ሲሆን ህዝቡን ለማሳወቅ ቅስቀሳ ማድረግ ግን አይፈቀድም አሉን። ህወሓቶችን ያስፈራ ጉዳይ የትግራይ አርሶአደሮች የብድር ብዝበዛ ያቀጣጠለው የህዝብ ተቃውሞ ነው። ቅስቀሳው ግን ይቀጥላል። ህዝብ አማራጭ ሐሳብ የመስማት መብት አለው። የህወሓት ዓፈና እንቃወማለን።

በሌላ በኩል ደቡብ ሕብረት-ኢሦዴፓ ፓርቲ ዛሬ ቅዳሜ መጋቢት 20, 2006 ዓም በሀዋሳ ከተማ ህዝባዊ ስብሰባ ጠርቷል። ዓረና ፓርቲም ተጋብዟል። የዓረና ተወካይ አቶ ካሕሳይ ዘገየ ንግግር ያደርጋል ተብሎ ይጠበቃል። ደቡብ ሕብረት -ኢሦዴፓ በደቡብ ክልል እንቅስቃሴ መጀመሩ የሚያኮራ ነው። የኦሮሞ ፌደራላዊ ኮንግረስ ፓርቲም በኦሮምያ ክልል ቅስቀሳ እንደሚጀምር ይጠበቃል።

↧
↧

“ከእናቴ በመጣላቱ ከቤት ወጥቶ ያልተመለሰው አባቴን አፋልጉኝ”–ቅድስት ሙላት ከሳዑዲ አረቢያ

$
0
0

የአፋልጉኝ ጥሪ

ተፈላጊ አባቴ ሙላት ገ/አምላክ ሃብተጊዮርጊስ በ1985 ዓ.ም ከእናቴ በመለያየታቸው ምክንያት ከቤት ወጥቶ የቀረ ስለሆነ ያለበትን አድራሻ የሚያውቅ ካለ ቢተባበረኝ በፈጣሪ ስም እጠይቃለሁ። በስልክ ቁጥር 000966530210347 ሊደውሉልኝ ይችላሉ።

ፈላጊ ልጅ ቅድስት ሙላት ገ/አምላክ – ሳዑዲ አረቢያ።

ዘ-ሐበሻ ይህችን መልዕክት በአየር ላይ ብታውሉልኝ ብዬ ነው።
afalegugn

↧

የፍቅሩም ሆነ ፍቱኑ መፍትሄ አሁንም ያው ነው። (ዳዊት ዳባ)

$
0
0

Penአንድን አገር  የመከፋፈል አደጋ የሚገጥመው  ስልጣንና መሳርያ የያዘው ክፍል በግድ የተሳሳተ አማራጩን ተፈፃሚ ስላደረገ ወይ በሚፈፅማቸው  ደባና ስህተቶች  እንዲሁ መገነጣጠል ፋላጎቱና አላማው ስለሆነ ብቻ አይደለም።  ለለውጥ የሚታገሉ ክፍሎች ሲበዙና  ልዩነታቸውን አቻችለው  በቀጣይ ሀላፊነቱን በጋራ ለመቀበል ሳይዘጋጁና  ችግሩን በአግባቡ ተረድተው መከላከያውን የሁሉን ቡድንና ዜጋ ፍላጎት በሚያስማማና በአንድ ሊያሰልፍ በሚችል ብለሀት ሰፊ የጋራ መፍትሄ ሊሰሩለት ሳይችሉ ሲቀሩ ነው።  በእርግጥም ያገራችን የወደፊት እጣ ፋንታ በጥሩ ወይ በመጥፎ ፍፃሜ የሚያገኘው በወያኔ ብቻ አይደለም። በድብቅም ሆነ በግልፅ ዘረኛ አጀንዳቸውን የያዙ ጎልበት ሲያገኙ ወይ ስልጣን ላይ ከተፈናጠጡ  አደጋው አይቀሬ ነው። ሁሉ በየዘሩ ተደራጅቶ ባለበት ያገራችን እውነታ ይሄ ወይም ያንኛው ክፍል አንድነቷ እንደተጠበቀ እንዲቀጥል የፀና ፍላጎታችን ነው ቢሉም በምንም ደረጃ የሚገለፅ ዘረኛና አግላይ አጀንዳ በጉያቸው እስከያዙ ችግሩን አጋግለው  የመጨረሻ ውጤቱ ተመሳሳይ ወይም የሚፈራው ነው የሚሆነው።  ዘረኛ ቢሆኑም ለህልውናችን ስጋት አይሆኑም የሚለው ፈሊጥ በኛ አገር ነባራዊ ሁኔታ አይሰራም።  ይህም ብቻ አይደለም ዘረኛ አጀንዳ ኖሮ አይደለም የሚመጣው ለውጥ ብዙና የተለያየ የሆነውን ሀሳብ፤ ፍላጎትና ስጋት የሚሸከምና አስማምቶ የሚሄድ  ካልሆነም አደጋ አለው።

የኛን አገር ሁኔታ ልዩ የሚያደርገው ኢትዬጵያ የምትኖረው እኛ ስልጣን ላይ እስካለን ብቻ ነው የሚሉ ዘረኛ ውላጆች ናቸው ስልጣኑ ላይ ያሉት።  ይህን አላማቸውን አልደበቁም። በጠራራ ፀሀይ ሁላችንም እንድናየው አድርገው እየሰሩበት ነው። በቀላሉ ተፈጻሚ ለማድረግ ያስፈልጋሉ ያሏቸውን ነገሮችን አመቻችተዋል። ላለመቀበል ካልወሰንን በቀር ይህንን ሁላችንም እናውቃለን። እንደውም ጠቅላላ ሁኔታዎች የሚያሳዩት ለውጥ መጥቶ ሳይጠራርጋቸው በፊት ይህን እኩይ አላማ ተፈፃሚ ለማድረግ ከጊዜ ጋር እየተሽቀዳደሙ እየሰሩበት እንዳሉ ነው። ለለውጥ የሚታገለው ክፍል እዚህ ያፈጠጠ ችግር ላይ ካለው ጠቅላላ ግንዛቤና የሰጠው ትኩረት ከችግሩ ክብደት አኳያ ባዶ ሊሰኝ የሚችል ነው።  ይባስ ብሎ የበዛው ዜጋም ሆነ ፖለቲከኛ ዘርን መሰረት ባደረገ እኛና እነሱ በሚል መነሻ ነው ጠቅላላ አገራዊ እይታው የተቃኘው። ስለዚህም ችግሩ ላይ ያለው መረዳት  ከተጨባጩ እውነታ በጣም የራቀ ነው። ያዋጣል ብለው እየሰራንበት ነው የሚሉትና የያዙት መፍትሄ የተሳሳተ መሆኑ ተደምሮ  ገዥዎቻችን የወሰኑ ጊዜ  በቀላሉ ይህን ተግባራዊ አድርገው እስታ ማለት  የሚከብዳቸው አይደለም።

ይህ አፈራራሽ አገራዊ ችግር የተለያየ ፍላጎት ቢኖራቸውም በለውጥ ፈላጊዎች በሙሉ ድርሻ በሚያደርጉበት ሰላማዊ የጠረቤዛ ዙሪያ ውይይት ከሚመጣ ስምምነት መፍትሄ ሊሰራለት ይገባል። ይህን ማድረግ ይቻላልም። በተወሰኑ ቡድኖች ዘረኝነት፤ጥላቻና ጠባብ እይታ ተውጠን ወይ ተሸንፈን ነው እንጂ ኢትዬጵያዊነት ሰፊ ነው። የማይመልሰው የመብት ጥያቄ፤ የማያካትተው ሀሳብ፤ የማይሞላው ፍላጎትና የማይሸከመው ልዩነት የለም። አፈጣጠሩም  ሆነ መሰረቱም ድሮም ቢሆን በልዩነት ላይ ነው። ብዙ በተሸከመ ቁጥር እየጠነከረ እንጂ እንዲዳከም ሆኖ ያለ አይደለም። ከንደዚህ አይነት ጥልቅ መረዳት የሚነሳ መፍትሄ  ስራው መጀመር ያለበት  ዛሬ ነው። ለነገ  ስንተወውና   አንድ ቀን ተኝተን ስንነሳ ብንን ብሎ ይጠፋል  የሚመስለው በብዙ ፖለቲከኞችና ተቆርቋሪ ዜጎች የሚራመድ ሀሳብ ስህተትነትም አደጋም እንዳለው ለማሳየት የሚሰማ ጠፋ እንጂ  በተደጋጋሚ ተሞክሯል።

ለጊዜው የሚያስከፍለውን ግዚያዊ ፖለቲካዊ ኪሳራ። ሊፈጠር የሚችለውና ጫጫታ ሳይፈሩ እዚህ አገራዊ ችግር ላይ በውይይትና በመቀራራብ የሚመጣ መፍትሄ  አገራዊ ፋይዳው ግዙፍ ነው።ትግል ላይ እንዳለ አንድ ክፍል መሰዋትነት በቀነሰ በቶሎ አሸናፊ ለመሆንም የተባበረ ሀይልን የመጠቀም ወሳኝነት ትክክለኛ ፖለቲካዊ እርምጃ አድርገው  ወስደውት የሞከሩት  በእርግጥ አሉ። እነዚህ ክፍሎች ከዚህ አትለፉ የሚለውን ያደጋ ምልክት ያለበት ማስፈራራት ተላልፈው  ለመቀራራብና ተባብሮ ለመታገል ሞክረዋል። ከዛም በላይ በውይይት ከሚመጣ መቀራረብ አንድነታችንን ባስተማማኝ ሁኔታ ለማስቀጠል የሚያስችል   መነሻ የሚሆን አንድ አይነት ስምምነት ለመቋጠር ጥረት ያደርጋሉ።

ሁላችንም እንደምናውቀው ማበላሸትና እንቅፋት መሆን እንደመስራት ከባድ አይደለም። ትናንሿንም ሙከራ ከስር ከስር እየተከታታሉ አምርረው የሚቃወሙና በተቀናጀና በተባበረ መንገድ እንዳይሳካ የሚሰሩ ነበሩ። አሁንም አሉ።  እነዚሁ ክፍሎች ናቸው ዛሬ ጎራ ለይተው እያየነው ያለነውን አደገኛ፤ ከፋፋይና አብሮነታችንን የሚገዳደር መዘረጣጥና እንኪያ ሰላንታ ውስጥ ያሉት። በጥቂቶች የተሞከረው ልዩነትን የማጥበብና የመተባበር ጥረት የራስ ዳሸንን ተራራ ያህል ገዝፎ ሲነገረን የነበረውን  የልዩነት ግንብ ሰብሮ እታች ህዝብ ውስጥ ድረስ የሚታይ  ትብብርን፤ አብሮነትንና ያንድነት መንፈስ ያጸና ነበር። በርግጥም ትክክለኛና ተስፋ ሰጪም ጅማሮ ነው።

በእርግጥ ይህ መፍትሄ ከዚህና ከዛ ወገን በተነሳ ተቃውሞ ቢደበዝዝም ዘረኛ ውላጆች ጉለበት ያገኙ በመሰላቸው ጊዜ ሁሉ የበለጠ ተፈላጊ፤ ፍጽም መፍትሄ ሆኖ ባብዛኛው ዜጋ ተቀባይ የሚሆን ነው። በርግጠኛነት ሞተ ሲሉ አፈር እየላሰ ይነሳል። ምክንያቱም ያገራችን ችግር ሌላ አቋራጭም መፍትሄም የለውም። በውይይትና በመቀራረብ  የሚመጣና ፍቅር የሚገለጽበት መፍትሄ  ላይ ስንደርስ ብቻ ነው  ነፃነታችንን የምናቀርበው። አንድነታችን አስተማማኝ መሰረት ላይ የሚቀመጠው። ይህን ማድረግ ካልቻልን ወደፊት መራመድ አይደለም አስከዛሬ ከሄድንበት ወይ ዝንፍች። ሲተውላቸው እንዴት እንደሚያጨማልቁት እያየን ነው።

አፅኖት ሰቶ ለተከታተለው በጥቂቶች በመለስተኛ ደረጃ የተሞከረው ለወደፊቱም  አገራዊ ችግሮቻችን ላይ አስተማማኝ መፍትሄ ለመስራት ትክክለኛውም የሚሰራው አንድና አንድ  ይህው መንገድ ብቻ መሆኑን ያየንበት ነው። መልካምና ትክክለኛ የነበረውን ጅማሮ የምር ተደርጎ ግን አልተያዘም፤  ዛሬ ጎራ ለይተው ለመላተም ቀንዳቸውን ወደታች ቀስረው በጎሪጥ እየተያዩ መሬት የሚደበደቡ ክፍሎች የሚያሰሙት ጫጫታ ሲበዛ በፅናት አልተቀጠለበትም። በቂ ክትትልና ያብዛኞቻችንን ድጋፍና እርብርቦሽ ስላላገኘ   ዛሬ  ለምናየው አፍራሽና አሳፋሪ አገራዊ ክስተት ቦታውን ሰጥቷል። ፖለቲካችን ዘር ተለይቶ  አንዱ ሌላው ላይ በሚያሳየው ጥላቻ ንቀትና ስድድብ ተሞልቷል። ወያኔን መታገል ተረስቶ የተጨቋኞች የርስ በርስ ልፊያ ትግል ሆኗል። በድጋሚ ለወደፊቱም ለነዚህ ክፍሎች የበላይነቱንና ተሰሚነትን እንዲያገኙ በፈቀድን ቁጥር የሚፈጠረው ዛሬ እየታዘብን ያለነው አፍራሽና አገዳዳይ ድርጊት እየጨመረ መሄድ ብቻ ነው። መዳረሻችንም የሚሆነው መከፋፈልና የዜጎች እርስ በርስ መጎዳዳት ነው።

ዘረኛ ውላጆች በድርጅታዊ ጥንካሬ ፤ በገንዘብ አቅም፤ ተከታዬችን በማብዛት፤በመገናኛው ዘርፍ። በሚያሳዝን ሁኔታ አንቱ የተባሉ ዜጎችን ምሁራንን አሰልፈዋል። ማሰለፍ ብቻ አይደለም እውቀታቸውን ሊዚህ አፍራሽ ሚና እየተጠቀሙበት ነው።  በአጠቃላይ እነዚህ ቡድኖች ሁለንተናዊ የበላይነት የያዙበት ፖለቲካዊ አየር ነው አሁን ያለው። ይህንን አይነቱን የበላይነት ያገኙት ሁሌም እርምጃቸው ውስጥ ሁሉ ዘረኝነት ስላለበት ነው። የዘር አቁፋዳቸው ውስጥ ያልከተተውን ስለሚያስፈራሩና ስለሚያገሉትም ነው። ሁሌም ሁሉን ነገር ሀላፊነት በሌለበትና በማን አለብኝነት ስለሚሰሩ ነው። ውሸትን አብዝተው  ይጠቀማሉ። የመጨረሻው ደረጃ ድረስ ወስደው ቆምንልህ የሚሉትን ዘር አባላት ሊበላህ ነው ጅቦ ይሉታል። ሽብር አብዝተው ይነዙበታል። የመልክታቸው ፍሬ ነገር ሲጨመቅ የዛ ዘር መኖር ለኛ መጥፊያችን ነው የሚመስለው።  ሁሉንም አጋጣሚ ይጠቀማሉ። አፄ ሚኒሊክን መቃወም አማራን ማጥቃት ነው። አፄ ሚኒልክን ማወደስ ኦሮምን ለማጥቃት አድርገው ይጠቀሙበታል። ታሪክን፤ የጋራ የሆነውን ጭቆና፤ በውድድር ያሸነፈ እስፖርተኛ፤ ወይ አገዛዙን የተጋፈጠን ጀግና…. ሳይቀር ዘሩን አጣርተው  ይጠቀማሉ። በተጨማሪ  ወያኔዎችም ጉልበት ሰጥተዋቸዋል። ስልጣን ይዞ ለመቀጠል ሁሌም ሲጠቀሙበት የነበረና ለወደፊቱም በእጅጉኑ የሚያስፈልጋቸው ስለሆነ  ይህን ማድረጋቸው  ግን አይገርምም። ቤንዚን በማቅረብና ክብሪት በመስጠት እየተባበሯቸው ነው። ሀውልቶች እየገነቡላቸው ነው። ጥንካሬውን እያገኙት እና ሀይል እየተሰማቸው እንደሆነ ሁለቱም ጎራዎች አውቀዋል። ዘረኝነት፤ ንቀትና ብልግና ልጓማቸውን በጥሰው እየቧረቁ ነው። ወንጀሉና ብልግናው አድጎ  እንደሁሌው ግለሰቦችና ድርጅቶች ወይም ቡድኖች ላይ ያለመና የሚያቆም አልሆነም።

ዳባ የሚል ስም ይዞ በዚህ ፖለቲካዊ አየር ይህን አይነት እውነት መናገር ምን ያህል ሚዛናዊ ተደርጎ ሊወሰድና ተቀባይ ሊሆን እንደሚችል ደጋግሜ እራሴን ጠይቄአለሁ።  ለወትሮው ሀይ የሚሉ ሰዎችን ብጠብቅ ዝምታን  ስለመረጡና ይባስ ተብሎ ጓሮ ጓሮውን ሲራመድ የነበሩ የከፉ ዘረኝነቶችና ጥላቻዎች ለለውጥ የቆሙ ወይም እኔንም ጨምሮ አብዛኛው ዜጋ የሚጠቀምባቸው መገናኛዎች ላይ ሽፋን እያገኘ ስለሆነ። ለዛውም  ሚዛናዊ ባልሆነና  በጥሬው  መሆኑን ስለታዘብኩ ልፅፍበት ተገድጃለው። ዘር እየጠሩና እየለዩ ህዘብ ላይ  የሚፈፀም አፍ መክፈትና  ወንጀል በየቀኑ እየጨመረ ነው። እውነትነት ስላለውና ሚዛናዊ ለመሆን ግን ለወትሮው በጅምላ አማራው እንዲህ ነው ከሚለው ወንጀል ዛሬ ዛሬ ኦሮሞ ወይ ሙስሊሙ የሚለው እጅጉኑ አይሏል። ይህን ምስክርነቴን ለመቀበል የተቸገረ ነገር ግን ነገሮችን ሁሉ አጥርቶ በማወቅና በሚዛናዊነት የሚያይ አንባቢ እንደጥቆማ ወስዶት አስተርጓሚም እየተጠቀመ ቢሆን ከዛሬ ጀምሮ የራሱን ክትትል ማካሄድ ይችላል። ድምዳሜው እኔ ከገለጽኩትም በላይ የሚያስደምም ሊሆን ይችላል።

ታላቅ በሆነው ኢትዬጵያዊነት ስር ተሸጉጦ  ለየትና ረቀቅ ባለ መንገድ የሚራመድ ዘረኝነት ለሌሎች ያለ ጥላቻ፤ ንቀትና ወንጀል  እየደባበቅነው ነው እንጂ የቆየና ስር የሰደደ ችግር ነበር። ነውም።  ዛሬ ለገባንበት ማጥ ውስጥም የከተተን ይህው ነው። ሀይላችንን አስተባባረን ዘረኛ አንባገነኖችን ከላያችን እናዳናራግፍ አላራምድ ብሎ በጭቆና ስራ እንድንኖር ካደረጉን ምክንያቶች አንድም ነው።  ፖለቲካዊ ችግሮቻችን ላይ ከዘመኑ ጋር የሚስማማ፤ ከጠረቤዛ ዙሪያ ውይይት  የሚወለድ ሰላማዊ መፍትሄ  እስቀምጠን ተባብረን  ነጻ እንዳንወጣና ወደ ብልፅግናው ጎዳና እንዳንገባ  እንቅፋት ነው። ይህን አይነቱን ዘረኝነትና የነዚህን ዜጎች  ወንጀል ዛሬ እነደከዚህ በፊቱ ለመሸፋፈንም ሆነ ለማስተባበል  የማያቻልበት ደረጃ ደርሷል።

ኢትዬጵያዊነት ትልቅም ጠንካራም ነው። ለረጅም አመታት በግልጽ በየጎጡ ተደራጅተው ዘረኝነትና ልዩነት ላይ የሚሰሩ ብድኖችን ማዳከም መቋቋም ችሏል። ስልጣኑ ላይ ያለው አገዛዝ  ዘረኝነትና አድሏዊነትን በከፋና ለማንኛችንም  በሚሰማና በሚያም መንገድ ለረጅም አመታት በሚራመድበት እውነታ ውስጥም ። አሁን ጉልበት እያገኘና እያገጠጠ የመጣው በሽፋንና በመሸጎጥ በዛ ላይ ከኛ በላይ ላሳር ኢትዮጵያዊ በሚል ማጭበርበሪያ የሚካሄድ ዘረኝነት ግን ሊያስከትል የሚችለው አደጋ በቶሎ ካልተገታ  በጭራሽ በጭራሽ ቀላል ሆኖ አልታየኝም። ለማንኛውም እስከሚቀጥለው ምርጫ የጥላቻና የዘር ፖለቲካ ናላችንን እንደሚያዞረን እንጠብቅ። ተቃዋሚዎች በሙሉ ደግሞ ከመቼውም ጊዜ በላይ ለዚህ ተመቻችተው ነው ያሉት። ለነገሩ ጣት ይቀሳሰራሉ እንጂ ሁሉስ መቼ ፅዱ ናቸው። ለማንኛውም በሚያናድድ ሁኔታ ከሂደቲ ተጠቃሚ ሆኖ የሚወጣው እንደሁሌው አርቆ የሚያቅደውና መጠቀምን የሚችልበት ይሆናል።

ዳዊት ዳባ Sunday, March 23, 2014 dawitdaba@yahoo.com

 

 

 

 

 

 

↧

ለጋዜጠኛ ፋሲል የኔአለም ብራቦ ብለናል (ከሥርጉተ ሥላሴ)

$
0
0

የወያኔ ማናቸውም የፖሊሲ አይነት ለነፃነት ትግሉ ምኑ ነው?

መልስ —– ምንም!  ከሥርጉተ ሥላሴ 29.03.2014 ሲዊዘርላንድ – ዙሪክ

1ይድረስ ለማከብርህ ወንድሜ ለጋዜጠኛ ፋሲል የኔአለም። ብራቦ ብለናል። ጥሩ መጠጋጋት ነው እንላለን እኔና ወዷ ብዕሬ። ወያኔን የምትደግፍበት አንድ ነገር መገኘቱ ሸጋ ነው – የሙያዊ ግዴታህ መንፈስ ካላስፈነጠረው። እኔ ደግሞ ይገርምሃል ወንድምዬ የዚህ ተቃራኒ ነኝ። በመጀመሪያ ነገር „ኢህአድግ“ የሚባል ነገር የለም። ኖሮም አያውቅም። ያለው ቲፒኤልፍ የትግራይ ሀዝብ ነፃ አውጪ ነው። ይህ „ኢህአድግ“ የምትለው ማላጋጫ ልባጅ ነው ወይንም ለጠፍ። ወይንም እቃ እቃ መጫወቻ የእንቦይ ካብ።  ለዚህ አቀብት ቁልቁለት የሚያስወርድ ነገር የለውም። በነቂስ እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ የሚውቀው ጠሐይ የሞቀው ጉዳይ ነው። በአንተ በታላቁ የተግባር አክቲቢስት ይህ ዕውቅና ወያኔ ማግኘቱ እጅግ ዕድለኛ ነው። በተከታታይነት ጭራዋን ይዞ በትጋት አፍኖ በያዘው ሰፊህ ህዝብ እዬሰረሰራ የሚገባ መርዝ አሳምሮና አስማምቶ ይረጭበታል። ለቀፎው የወያኔ ሚዲያና የጎሳ ጥመኞች ጥሩ አልጋ አዘጋጅተኽላቸዋል። በደሉ እራሱ፣ አስከዛሬ የፈሰሰው ደምና ዕንባ ሁሉም አፍ አውጥቶ ቢናገር ፍርዱ ዬት ላይ ሊሆን እንደሚችል ማዬት በተቻለ። …. ለነገሩ ትክለኛው የህሊና ዳኝነት ያለው በህዝብ የህሊና አደባባይ ስለሆነ ልተወው።

 

የማከብርህ ወንድሜ ጋዜጠኛ ፋሲል እንዲህ የቤታችሁ ሥራና ውጥረት መፈናፈኛ ሰጥቷችሁ ነው የወያኔ የመሬት ፖሊሲ አስጨንቆህ ድፍት ብለህ ስትጽፍ ያደረከው? ለዛውም ለማይመለከተን፣ ላልመከርንበት፣ ብስል ከቀሊል ለሚለይበት፣ ላልወሰንበት፣ በባይታወርነት ለምነቀጠቀጠበት የኢትዮጵያን ሙሉ የክብር አካል ለሚፈቀፍቅ ፖሊሲ። አጀብ ነው። ከቶ እኛን ምን አገባን?!

ጨዋታን ጨዋታ ያነሳዋል የሚል አንድ ብሂል አለ። አንድ ጊዜ ጠ/ ሚ ሃይለማርያም ደስአለኝ የሟቹን ሄሮድስ መለስ ዜናው ግዛታዊ ግቢ ሊረከቡ በነበረው የመሰናዶ ወቅት ጸሐፊ ተስፋዬ ገብሬ ድምጽ ሆነ ምስል በሚስጥር የሚቀርጽ ነገር በቤተመንግስቱ ወያኔ እንደሚያሰቀምጥ ማጠቀሻ መረጃ ጨምሮ ጽፎ ከረንት ከቤቴ አንብቤ ነበር።

2ታዲያ እኔ እህትህ ያን ጊዜ እኛን ምን አገባን?  ….. ብዬ ከሥር ጠንከር ያለ ትችት መጻፌን አስተዋሳለሁ። አሁን ደግሞ አንተ መሰሉን ነው የምትነግረን። ግልጽነትህ መቼም የሚገዛ ቢሆን ቀዳሚ ተሰላፊዋ እኔ በሆንኩ በነበረ። ለዚህ ከልብ ለጥ ብዬ አስግዳለሁ – አመሰግናለሁ። ውስጥህን ፈቅደህ ማሳዬትህ የማይገኝ ነው። ወደ ዋናው ጉዳዬ ስመጣ ግን  እኛ ስለ አይሁደ የመሬት ስሪት ምን ዶል አደረገን? ስለ በቀለኛው ባንዳ የፖሊሲ አፈጻጸም ሳይጠሩንስ የምን ዝንቁል ነው? ለምንስ መቀላቀል አስፈለገ?


ግን መሬት የኢትዮጵያ የእኛ የምንለው አለን?! አሱን አጥተን መስሎኝ የተሰደድነው። መቼም አንተም እንደምታወቀው 90 ሚሊዮን ህዝብ ልሰደድም ልሸፍትም ቢል አይችልምና አሁንስ መፈናፈኛ አጥቶ ከቀዩ ስለሚፈናቀለው፤ ሞት ለተፈረደበት ሚሊዮን ወገንህስ ታሰረኸለት – ተሰደኸለት – መሰደድህ አልበቃ ብሎ የመጨረሻውን ፍርድ ተቀብለኸበት እንዴት ነው ነገሩ ….. ወንድምዬ? እኔ እህትህ እንድ ሥርጉተ ሥላሴ መንፈስና አቋም ግን የወያኔ ማናቸውም ፖሊሲ በለው፤ ህግ በለው፤ የአፈጻጻም ደንብ በለው፤ ህግ አርቃቂ አካል – አስፈጻሚ ተቋም፣ የዳኝነት ውሎ ድል ምንጥርስ ቅብጥርስ ከነምናምንቴው  ወዘተ ምኔም አይደለም። ቆራጣ ጊዜ አላባክንም። እኔይቱ ላለተርፍበት እማባክናት ብጣቂ ጊዜ የለችኝም። ወያኔ ታጥቆ ስለተናሳበት የጥፋት፤ የንደት፤ የውርስና ቅርስ ፍልሰት ጥብቅናም ልንቆምለት ይገባል ባይም ነኝ። የ40 ዐመቱ ጉዞና ግብዕቱ መሰረቱ አንድ ነው። የቲፒኤልኤፍ የጎጥ ማኒፌስቶ። በቃ! ከዚህ የሚያመልጥ የሰናፍጭ ታክል ነገር የለም። ሁሉም የሚመነጨው ወያኔ ከተነሳበት አላማ ነው። ማናቸውም ህግ በለው ፖሊሲው መርዝ ነው። ከዚህ በተረፈ ማንፌስቶውን የፈጠረውን „ብርቱ ሚስጢር“ እንደ እኔ እንደ ደንቆራዋና ምስኪን ሳይሆን እንደ ታሪክ ሙሁርነትህ፤  እንደ ጋዜጠኝነትህ እንደ ታላቅ የሚዲያ አስተዳዳሪነትህና ኤዲተርነትህ እባክንህን እናትዬ  ብትን አድርገህ መንፈስ ሰሌዳ ላይ አደላድላና ብልቱን አውጣው። መልሱን ታገኘዋለህ። ባለፈም እንደ እኔ ላላ ማህይም ህሊና ዘባ ሲል ጎባጣውን አቃንተህ ትገራበታለህ።

 

4ወንድምአለም ቀድሞ ነገር ኢትዮጵያ ዕውን አለችን ነው ጥያቄው? ለመቶ አመት እኮ እየተቸበቸበች ነው? ከመቶ አመት በኋላም መሬቱ ዘር ስለመሰጠቱ መዳህኒአለም ይወቀው። ዛሬ እንዲህ ቅዱሳኑ ይከላተማሉ። ይሄውልህ ልጁህ ግልገሉን ይዞ መድረሻ አጥቶ እንዲህ ይንከራተትልሃል። ውሎ አድሮም ለትውልዱ ይህን ተከትሎ የሚመጣው ፍልሰትና ቀውስም ዕዳ ነው ልትሸከመው የማትችለው። ረመጥ እያደረ እዬፋመ እያገላበጠ የሚቀጣ ይህ ነው የተዶለተልህ።

ወይ ጉድ! ዘር እንዳይራባም እኮ ወያኔ መላ መቷል።   በታላቋ ትግራይ ህልም ደግሞ ከአፋር የደካ ጎንደርን ወሎም አለፍ ብሎ የአባይን ኣናት ጭምር ለመቆጣጠር እንዲያስችል ሌትና ቀን እዬተሰራበት ነው። መንገዱ ከጁቡቲ ትግራይ፤ ከሱዳን ትግራይ ጦፏል፤ እና …. ከአሲድ ጋር የሚያደራድረን ከቶ ምን ብናኝ  ነገር አለና?! — ቅድሚያ ነጻነት —- ንጹህ አዬር። ከሥጋት የጸዳ ባዕት —–

 

በወያኔ ፖሊሲ ለኢትዮጵውያን ለዛ መሬት ለተደፋበት ብዙኃን ተቆርቋሪ የሆነው የትኛው ተቋም፤ ድርጅት ከቶ የትኛው ነው? የትኛው ይሆን ኢትዮጵያዊ ኢትዮጵያዊ  የሚሸተው? ሰንደቅን የሚያደምጥ ፍላጎትና ዝንባሌ እስረኛ እኮ ነው። – በጠቅላላ የወያኔ ፍትረት የጠላትነት ነው። ለእኛዎቹ እኮ መስቀል አደባባይ የታጠረ ነው። ስለ አፓርታይድ የመሬት ፖሊሲ እንደ ፍጥርጥሩ እሱ ይፈናጠርበት ጎጠኛው ወያኔ … ለምርጫም – ለበጎ ነገርም – ለድርድር የሚያበቃን ነገር ቅንጣት የለም? የውጭ ባዕዳን ፍላጎት አስፈጻሚ የባንዳነት ተልዕኮ እኮ ነው የወያኔ ተግባር።

እርግጥ ነው እንደማንኛውም የጥበብ ሰው ቀድመው የሚያሰጉትን ነገሮች ማመላከት የተገባ ነው። ይህን አከብርልኃለሁ። ነገር ግን ሰለ ነገ የመሬት ድርሻ ወይንም የባለቤትነት ይዞታ አስጨንቆህ ከሆነ የምንፈልገው አይነት የዴሞክራሲ ሥርዓት ሲዘረጋ በህዝብ ድምጽ አዎንታዊ ይሁን አሉንታዊ ምላሽ ያገኛሉ። ድምጽ የሚመራት ሀገር ስትኖርን። የማትቦጫጨቅ የእኩልነት እናት ምድር ስትኖረን። ለዚህ ቢያበቃንም ችግሩ የአዬለ ስለሆነ በቂ ጊዜ፤ የሰከነ ጥናትና ተግባርን ይጠይቃል። እፍ ብላህ ከምድረ ገጽ የምታበነው ችግር አይጠብቅም …. ዳገት ነው -።


እናቴ እመቤቴ ልዕለቴ የሚል እረኛ ሲኖረን፤ ይህ ዝበትና አድሎዊነት ሁሉ ታርቆ በሂደት መልክ ይይዛል። ይስተካከል። ፕሬዚዳንት ክርሰቲና ክሪሸርን የአርጀንቲናዋን፤ ጠቅላይ ሚኒስተር አንጅላ ሜርክልን የጀርመኗን፤ ፕሬዚዳንት ባራክ ኦባማን ለሥልጣን ያበቀው ሥርዓቱ ስለተዘረጋ ብቻ ነው።

… የድካሙ የትግሉ አቅጣጫም ይህ መሆን አለበት እንጂ ይሄኛው ያኛው እያልን በሳቢያዎች ላይ የምናጠፋውና የምናባክነው ጊዜና ጉልበት ሊኖር አይገባም።  ዘላቂ የመፍትሄ ቁልፍ ሊሆን ከቶውም አይችልም። እንዴት ነው ነገሩ ኢትዮጵያ እራሷ አኮ እስረኛ ናት – የምን ቀልድ ነው!? ከወገብ በላይ ከወገብ በታች ብሎ ትግል የለም። የነፃነት እርቦ ሆነ ሲሶም የለም። ግድ የለህም ወንድምዬ እንስማማ። ምክንያትን እንፈልግ፤ የምክንያትን አቅጣጫ እንመትር በዛ ላይ አቅም የሚመትን ተግባር እንከውን …. ሳቢያን እንዝጋው – ቅርቅር አድርገን።

 

የማከብርህ ጋዜጠኛ ፋሲል እኔ በአቀረብካቸው የመሬት ይዞታ የፖሊሲ ትንታኔና አቅጣጫ ደንቆሮ ስለሆንኩኝ ባለሙያዎቹ እንደ አመጣጡ ይመክቱህ። ግን ጠላቴ ማን እንደሆን አውቃለሁ። የጠላቴ ፍላጎት እንብርት ምን እንደሆን ጠንቅቄ እረዳለሁ። ጠላቴ ለሀገሬ ኢትዮጵያ ያለውን ጠናና አመለካከት አሳምሬ እረዳለሁ። የበሽታው አጠቃላይ አስኳል ዬት ላይ እንዳለ ይገባኛል። በቀዶ ጥገናም ፈውስ እንደማይገኝ አምናለሁ። የመፍትሄው ቁልፍ ሂደት ወሳኙ አካል ምን ስለመሆኑም መንፈሴ በቂ ጥግ አለው።

በተጨማሪም አቅም ምን ላይ ሊፈስ እንደሚገባ ሆነ እንዲሁም ጉልበትና ሃይል ሊፈጥሩ የሚችሉ የመንፈስ ሃብቶች መሰናዶ  ምንና ምን  ሰለመሆናቸው ጠንቅቄ አውቃለሁ። ስለዚህም እላለሁ ለኢትዮጵያ ዘላቂ ትንሳኤ የወያኔ ማንፌስቶና ፖሊሲ እሰከ ዝክንትል ጓዙ መነቀል አለበት የሚል ጽኑ እምነት አለኝ። ለቅርጥምጣሚ መላሾ የሥርጉተ መንፈስ አያደገድግም …. ኢትዮጵያ የመተንፈሻ ቧንቧዋን አፍኖ በጠላትነት እዬታገላት ያለው መጋኛ ወያኔ ሲወድቅ የቀደሙ ይሁን አሁን ያሉ፤ ወደፊትም ዘምን ሊፈጥራቸው የሚችሉ ችግሮች ሁሉ በመመካካር – በመደጋጋፍ – በመደማማጥ ፈቃዱ ሲሆን የተባረከው ቀን ሲመጣ ሁሉም ያለውን ይዞ እናቱን ከወደቀችበት ማጥ ለማውጣት በቅንነት ወስጥጡን ሰጥቶ የሚሳተፈበት ሥርዓት ሲፈጠር በጣም በእርግጠንነት ከኢትዮጵያውያን አቅምና ቁጥጥር በላይ የሚሆን አንዳችም ችግር አይኖርም።

 

የሚያስደስኝ በወያኔ ቅንጥብጣቢ መንፈሳቸው የማይደለል ጀግኖች ወጣቶች ኢትዮጵያ ላይ መኖራቸው። አይገርምህም ወያኔ ሲገባ ያልተወለዱ ልጆች የፈካ የተስፋ እርምጃ፤ የጎለበት አቅም፤ የራዕይ ጉልበት፤ የጸደቀ መንፈስ፤ የቁርጠኝነት ትንታግነት፤ የጥራት ልዕልና፤ የአስተሳሰብ ሥልጡነት፤ የመንገድ መረጣ ስልታማነት፤ የፈጠራ እርካብን – የአፈጻጻም ሂደቱ ለምነት፤ የሀገር ፍቅርና የአብሮነት ሰማዕትንት፤ እርግጠኝነትና በራስ የመተማማን ሙሉ ብቃት ሙቀቱ ከበቂ በላይ አጥጋቢ ነው። እነዚህ የትናንት እንቡጡች ወያኔ ሲገባ ታቱ ዥግራ ወይንም በእምዬ ትክሻ አንቀልባ የነበረቱ፤ ወይንም የአንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪዎች የነበሩት ራህብ ላይ ሆነው፤ አንጀታቸው ጠግቦ ሳያድር  „ሰንድቅአላማ“ በተሳረበት ዘመን አድገው፤ ትምህር ቤት ዜግነታቸውን የሚሸረሽር ሥልጠና እዬተሰጣቸው፤ ነገር ግን ያነን ሁሉ አሸንፈው „አትከፋፍሉን፤ አትለያዩን፤ አንድ ነን፣ አንድ ህዝብ፣ አንድ ሀገር“ ይላሉ ለዚህም ይታሰራሉ – ይገረፋሉ – ይሰደዳሉ፣ ይገለላሉ- ይወቀሳሉ – ተነጥለው ይጠቃሉ። ግን መከራውን እያሸነፉ ወደፊት እዬገሰገሱ ነው —- ከዚህ መርዛማ የወያኔ ዶክትሪን አምልጠው እኛን በተግባር እያስተማሩን ይገኛሉ። የትውልዱ መንፈስ ይህ ነው አድምጡን ይላሉ ጆሮም ህሊናም ከኖረን …..

በዚህ በምታዬው የክልል ሽንሸና የኢትዮጵያዊነት መንፈስ ለመቅበር የተዶለተበት ነበር። ግን ኢትዮጵያዊነት ጠፍቶ የማይጠፋ የነገ ፍቱን መዳህኒት በመሆኑ የተጫነውን ድንጋይ ፈንቅሎ እዬፈካ በቀንበጦቻችን ታዬዋለህ …..

3

እኔ ውጪ ላላውም ወገኔ ቢሆን የተፈጠረበት ሚስጥር ነፃነት በመሆኑ ያገባኛል ባላበት ጉዳይ ሁሉ ተግቶ መሳተፉ፤ ሀገሩ ኢትዮጵያን በዬትኛውም አጋጣሚ ጎላ ብላ እንድትታይ መባተሉ፤ ክብሯ ሲነካ እሳት ለብሶ እሳት ጎርሶ በቁጣ ከጥንፍ አስከ ጥንፍ መነሳቱ – ከሌሎች ሀገሮች ጋር ሲነጻጻር ሚዛን ላይ ልታስቀምጠው የማትችል የበቃ – ብቃትን ታያለህ። እርግጥ ስደትና ትግል ሰፊ ፈተና በመሆኑ የሚታገሉን በተርካታ ነገሮች በመኖራቸው፤ በተጨማሪም ከድሉ መዘግዬት ከሚመጡ ጭብጦች ጋር ያሉ ወጣ ገብ ጉዳዮች እንዳሉ ሆነው ማለቴ ግን ብርቱዎች ነን የእውነት።

ለዛውም አንተም እንደምታውቀው የፖለቲካ ትግል በትርፍ ሰዐታት ሰርተህ አይደለም ትርፍ የምታስገኘው። በመደበኛና በቋሚነት ተቀጥረህ የምትሰራው ሆኖ፤ ግን ነገር ግን ተስፋ የሚሰጡ ነገሮች ታያለህ። አንተ የምትደክምለት ሚዲያ ኢሳትም የዚህ ውጤት ነው።  በአጋጣሚ ስለሚዲያው ስለ ኢሳት ካነሳሁ በንጉሦች ንጉሥ ዐፄ ሚኒሊክ የልደት በዐል አስመልክቶ በተነሳው የሃሳብ በለው ድንበር ዘለል ጦርነት በነበራችሁ ውይይት በተጻራሪው ወገን የነበረውን ኮበሌ የሚመጥን ሰው አላቀረባችሁም ነበር። እባካችሁ የሚመክት ብቃትን በሃሳብ ማታገል አድማጭን ወደ በሰለ የሃሳብ መቀራርብ ያመጣልና ጥንቃቄ አድርጉበት። አቅም ማለት እኮ ሃሳብህን የሚሸምት ሰራዊት ማግኘት ማለት ነው።

 

እንድ መቋጫ ወንድሜ ጋዜጠኛ ፋሲል ሙሁራኖቹ ጭብጥን በጭብጥ ማህሏን እያስቀመጡ ይሟገቱህ።  እኔ ማሃይሟ ደግሞ በሀገር ወዳድነት ህልምና ናፍቆቴን ብቻ ስሜቴን አቅርቤ ሃሳቤን ገለጽኩኝ። ለነበረን ጊዜ ምስጋናዬ ከፍቅራዊ እክብሮት ጋር ላኩኝ። በተረፈ ክብረቶቼ ይሄውላችሁ ልጅ ፋሲል የማትመቸኝን ነገር ኮልኩሎ ለዛሬ ያቀድኳትን ጊዜ ተሻማኝ – እናንተንም አደከምኩ ከሳምንት በፊት ብቅ ላል ወስኜ ነበር — ለሰጣችሁኝ ጊዜ ውስጤን ፈቅጄ ሰጠኋችሁ። መልካም ጊዜ።

 

ከ አሲድ የሚገኝ ዘርም ፍሬም የለም!

ኢትዮጵያዊነት ፈተናን አሸንፎ የተፈጠረ ሚስጥር!

 

እግዚአብሄር ይስጥልኝ!

 

 

 

↧

በነገሌ ቦረናው ግጭት ከ30 ሰዎች በላይ ተገድለዋል፤ ግጭቱ አልቆመም

$
0
0

ነገሌ ቦረና (ፎቶ ፋይል)

ነገሌ ቦረና (ፎቶ ፋይል)


ምንሊክ ሳልሳዊ ፦ በደቡብ ኢትዮጵያ በነገሌ ቦረና ከከተማው ስም ስያሜ ጋር በተያያዘ በጉጂ እና በቦረና ማህበረሰቦች መካከል በነገሌ ቦረና አካባቢ በተነሳ ግጭት ከ30 ሰዎች በላይ መሞታቸውን እና ግጭቱም አለመቆሙን የአከባቢው ባለስልጣናት ምንጮች ማምሻውን በላኩልን መረጃ ገለጹ። ከባለፈው እሁድ ጀምሮ በአከባቢው የተነሳው ግጭት በመስፋፋት ከፍተኛ የሆነ ንብረት ያወደመ ከመሆኑም በላይ ከነገሌ ከተማ ውጪ ለጉላ እና አርዶታ በተባሉ አከባቢዎች ግጭቱ ተስፋፍቶ መቀጠሉ ታውቋል። ከዚህ ጋር በተያያዘ ወደ ግዛቴ ግጭቱ ዘልቆ ሊገባ ይሽላል በሚል ፍራቻ ኬንያ ወታደሮቿን በድንበር አከባቢ አስፍራል እያስጠበቀች መሆኑ ታውቋል።

የኢሕአዴግ ፌዴራል ፖሊሶች እና የኦሮሚያ ክልል ልዩ ሃይል ፖሊሶች በቦታው ደርሰው የነበረ ቢሆንም የአከባቢው ህብረተሰብ ቀየውን በመልቀቅ እየተሰደደ መሆኑን ታውቋል። በከፈትና ፍጥነት እየተስፋፋ የመጣውና የጎሳ ፌዴራሊስም ፖለቲካ ውጤት የሆነው ይህ ግጭት በአካባቢው ባለስልጣናት እና የሃገር ሽማግሌዎች ለመፍታት ቢሞከርም ሳይሳካ ግጭቱ እንደቀጠለ ታውቋል።

↧
↧

ሚሊዮኖች ድምጽ –የነጻነት ደዉል በአዲስ አበባ፣ በአዋሳ እና በደሴ ተደዉሏል!

$
0
0
MILLIONS OF VOICE FOR FREEDOM !

አንድነት ፓርቲ

የአንድነት ፓርቲ ሰላማዊና ሕጋዊ በሆነ መንገድ የሚንቀሳቀስ ድርጅት ነው። በኢትዮጵያ የፌዴራልም ሆነ የክልል ባለስልጣናት የተለያዩ ሕጎችና ደንቦች ሊያወጡ ይችላሉ። ነገር ግን ሕገ መንግስቱ የሕጎች ሁሉ የበላይ ነው። በሕገ መንግስቱ የተቀመጡ መሰረታዊ የሕግ አንቀጾችን ማንኛዉም አካል ሊሽረው ወይንም ሊቀለብሰው አይችልም።

የኢትዮጵያ ሕገ መንግስት አንቀጽ 30 ዜጎች ነፍጥ ሳይዙ የመሰባሰብ፣ ሕዝባዊ ሰላማዊ ሰልፎች የማድረግ፣ ፔትሽኖችን የማሰባሰብ ሙሉ መብት እንዳላቸው ይደነግጋል።

“Everyone shall have the freedom, in association with others, to peaceably assemble without arms, engage in public demonstration and the right to petition. Appropriate procedure may be enacted to ensure that public meetings and demonstrations do not disrupt public activities, or that such meetings and demonstrations do not violate public morals, peace and democratic rights.”

ይላል አንቀጹ።

በአዲስ አበባ፣ በደሴና በአዋሳ ሰላማዊ ሰልፎች ይደረጋሉ። በሰልፉ የጥበቃ ኃይላት ያሰማሩ ዘንድ ለባለስልጣናት አስፈላጊዉ የማሳወቅ ደብዳቤ ተልኳል። በታሰበው ቀንና ቦታ ሌሎች እንቅስቃሴዎች ካሉና በቂ የጥበቃ ኃይል ማሰማራት ባለስልጣናት ካልቻሉ፣ ቀኑ እንዲራዘም ወይንም የሰልፉ ቦታ እንዲቀየር ሊጠይቁ ይችላሉ። ከዚያ ዉጭ ሰልፎችን የመፈቀድም ሆነ የመከልከል መብት ባለስልጣናት የላቸውም። ይሄ መታወቅ አለበት። ከከለከሉ ወይንም መፍቀድ አለብን ካሉ፣ በቀጥታ የአገሪቷን ሕግ ያፈርሳሉ ማለት ነው። ሕገ ወጥ የሚሆኑት እነርሱ ናቸው ማለት ነው።

ሰልፍ ማድረግ አመጽ አይደለም። የአንድነት ፓርቲ፣ የሰማያዊ ፓርቲ ላለፉት በርካታ ወራት የተለያዩ ሰልፎች አድርገዋል። በሰዉም ሆነ በንብረት ላይ አንድም ጉዳት አልደረሰም። ከፖሊሶች ጋር ምንም አይነት ግብግብ አልተፈጠረም። አንዲት ጠጠር አልተወረወረችም። ኢሕአዴጎች ይሄን ልብ እንዲሉ ያስፈልጋል። እነርሱ ሌላው ሕግ ማክበር አለበት እንደሚሉት፣ ሕግን ማክበሩ ያዋጣቸዋል።

እንግዲህ ሁላችንም እንዘጋጅ፤ ዉስጥ ውስጡን ማጉረምረም ይበቃናል። እርስ በርስ ማንሾካሾክ ይበቃናል። ከሚሊዮኖች ጋር ሆነን ድምጻችንን በድፍረት፣ በአደባባይ እናሰማ። ፈርተን እና ተስፋ ቆርጠን ከተደበቅን፣ ከሸሸን፣ ዝምታን ከመረጥን፣ በሙስናና በመልካም አስተዳደር እጦት የተዘፈቁት ገዢዎቻችን የደገፍናቸው ነው የሚመስላቸው። እንነሳ፣ እንቀሳቀስ። ሕገ መንግስቱ ይፈቅድልናል። ኢትዮጵያዊ የዜግነት ግዴታም አለብን።

እኛ ጥይት አንተኩስም ! ጠጠር እንወረወርም! ጥላቻን አንዘምርም። ክርስቲያን፣ ሙስሊም፣ ኦሮሞ፣ ትግሬም፣ አማራ፣ በብሄረሰቡ መታወቅ የማይፈልገው ቅልቅሉ..…ሁላችንም፣  በዘር፣ በኃይማኖት ሳንከፋፈል፣ ሚሊዮኖች ሆነን ድምጻችንን እናሰማለን። በርግጠኝነት የሚሊዮኖችን ጥያቄ ሊንቅ የሚችል ማንም ኃይል የለምም፣ ሊኖርም አይችልም።

እንግዲህ የነጻነት ደዉል በአዲስ አበባ፣ በአዋሳ እና በደሴ ተደዉሏል። ጥሪ ቀርቧል። ትኩረቱ ወደነዚህ ከተሞች ይሆናል!!!!!

በላስ ቬጋስ፣ በአትላንታ እና ዴንቨር የሚኖሩ ኢትዮጵያዉያን እነዚህ ሶስት ከተሞችን ስፖንሰር በማድረግ ድጋፋቸውን በመግለጻቸዉ ሊመሰገኑ ይገባል። ሌሎቻችንም ተደራጅተን፣ ሶሊዳሪቲ በማሳየት የሚሊዮኖች አንዱ እንሁን !

 

እንበርታ ፣ እንጎብዝ ! ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ !

millionsforethiopia@gmail.com

↧

ስለመሬት መሸጥ መለወጥ -ተጨማሪ ማብራሪያ (ፋሲል የኔዓለም)

$
0
0

 

ጋዜጠኛ ፋሲል የኔዓለም

ጋዜጠኛ ፋሲል የኔዓለም

ውድ ስርጉትና ሌሎች አስተያየት ሰጪዎች የጽሁፌን ይዘት በደንብ ባለመረዳት ይመስል “ የምን ጠጋ ጠጋ” ብለውኛል። እኔና ኢህአዴግ ከምንጠጋጋ ጸሃይና መሬት ቢጠጋጉ ይቀላል። ወያኔን የምደግፍበት አንድ ነገር አገኘሁ ማለቴ ስላቅ ነው። ወያኔ መሬት አይሸጥም አይለወጥም ይላል። ይህን ያለው ከ20 በፊት ነው። ዛሬ ግን በሙሉ ልቡ ደፍሮ እንደዛ አይልም። ለምን? ያን ጊዜ የህወሃት ሰዎች ገንዘብ አልነበራቸውም። ዛሬ ግን የአገሪቱን መሬት ጠቅልለው የሚገዙበት ገንዘብ አላቸው። ዛሬ መሬትን በግል አዙር ብንለው መሬቱን እነማን እንደሚገዙት እናውቃለን። በ20 አመት ፖለቲካ ማሰብ የለብንም። ብዙ ህዝብ አገራችን ያለችበትን ሁኔታም የተረዳ አይመስለኝም። ዛሬ ገንዘቡ ኢፈርት በተባለው በህወሃት ድርጅትና በአላሙዲ ስር ነው ያለው። መሬት ወደ ግል ቢዞር እኮ የሚገዙት ሁለቱ ናቸው። እና 90 ሚሊዮኑን ህዝብ ባሪያ እናድርገው። ወያኔን ታግሎ መጣልና አዲስ መንግስት ማቋቋም ተገቢ ነው። አሁን መሬትን ወደ ግል አዙር እያልን ከጨቀጨቅነው ግን በደስታ ያዞርና ሌላው ህዝብ የዝምባብዌ ወይም የደቡብ አፍሪካ እጣ ይገጥመዋል።

 

አንዳንድ ሰው ስለ አዲሱቹ ካፒታሊስቶች የገባው አልመሰለኝም። ኢትዮጵያ እኮ የደቡብ አፍሪካ አይነት የኢኮኖሚ ስርአት እየገነባች ነው። በዘር ላይ የተመሰረተ ስርአት።

ለማንኛውም ለሌሎች አስተያየት ሰጪዎች የሰጠሁትን መልስ እዚህ ላይ እንዳለ አትሜዋለሁ። የአቋም ለውጥ ያደረኩ የሚመስላችሁ ካላችሁ ጽሁፌን እንደገና እንድታነቡት እመክራለሁ።

 

“ዳዊት ሰለሞን የተባለው ሰው በመሬት ዙሪያ ለጻፍኩት መልስ ሰጥቷል። አመሰግናለሁ። እኔ ከ20 አመት የኢህአዴግ የስልጣን ጊዜ በሁዋላ የተገለጠልኝ ሃሳብ እንደሆነ፣ ቀደም ሲል መሬት እንዲሸጥ እንዲለወጥ ስፈልግ እንደነበር የሚያስመሰል ሃሳብ አቅርቧል። ያነሳቸው ሃሳቦች ብዙም ጠናካራ ሆነው ባላገኘኛቸውም፣ ለትምህርት ይሆነን ዘንድ ትንሽ ለማለት ፈለኩ።

 

ቀደም ብየ እንደገለጽኩት መሬት ወደ ግል እንዲዞር ከሚፈልጉት መካከል ነኝ። ነገር ግን በዚህ መንግስት መሪነት የሚደረግን ክፍፍል አልደግፍም። ዶ/ር ታደሰ ብሩ ኢህአዴግ መሬት ወደ ግል መዞሩ ኢህአዴግን ቢጠቅመው ኖሮ እስካሁን ያደርገው ነበር በማለት መሬትን ወደ ግል ማዞር ለፖለቲካው እንደሚጠቅም ገልጿል። የዳዊትም ሃሳብ ተመሳሳይ ይመስላል። የእኔ ሃሳብ ደግሞ መንግስት መሬትን ወደ ግል እንዲያዞር ከመጠየቅ ፣ ስርአቱን ቶሎ አስወግዶ በዲሞክራሲያዊ መንገድ የሚቋቋመው መንግስት ፍትሃዊ በሆነ መንገድ ያከፋልፍ የሚል ነው።

 

ኢህአዴግ  መሬት ለማከፋፈል ለምን አልፈለገም? ብዙ ሰዎች ህዝቡን ለመቆጣጠር ስለሚመቸው ነው ብለው ምክንያት ይሰጣሉ። ሊሆን ይችላል። ነገር ግን መሬት ወደ ግል ቢዞርም ኢህአዴግ ሌላ የመቆጣጠሪያ ዘዴ መፍጠሩ  እንደማይቀር ማወቅ አለብን።   ለእኔ ዋናው ምክንያት ኢህአዴግ የራሱን ካፒታሊስቶች እስኪፈጥር ጊዜ ለመውሰድ ስለፈለገ ነው። ባለፉት 22 አመታት ወያኔ በአንድ ዘር ላይ የተማከለ ካፒታሊስቶችን ለመፍጠር ከፍተኛ ጥረት አድርጓል። በስልጣን ላይ እስካለ ድረስም ይህንን ስራውን ይቀጥልበታል። ካፒታሊስቶች በቂ ሀብት አጠራቅመው አገሪቱን ሙሉ በሙሉ  የሚቆጣጠሩበት ደረጃ መድረሱን ወያኔ ሲረዳ ፣  ማከፋፈሉ አይቀርም። ምክንያቱም መሬት  ወደ ግል ቢዞር መሬቱን የሚገዙት እነዚህ ካፒታሊስቶች ይሆናሉና። ይህ አካሄድ ደግሞ የአገሪቱ መሬት በጥቂት ካፒታሊስቶች እጅ እንዲወድቅ ያደርጋል። እነዚህ ካፒታሊስቶች ደግሞ በአብዛኛው የአንድ አካባቢ ሰዎች ናቸው። ወደድንም ጠላንም አብዛኛው መሬት በእነሱ እጅ መውደቁ አይቀርም። መሬት በመንግስት ስር ከቆየ ግን አዲሱ መንግስት  ሲመጣ በቀላሉ ይነጥቃቸዋል። አዲስ መንግስት ከመምጣቱ በፊት መሬት ወደ ግል ቢዘር  ፣ የሚመጣው መንግስት ጦርነት የሚገጥመው ከእነዚህ ካፒታሊስቶች ጋር ይሆናል።

 

መለስ በአንድ ወቅት  “መሬትን ወደ ግል ብናዞር መሬቱን የሚገዙት እነማን እንደሆኑ እናውቃለን፣ ሌላው ህዝብ መሬት የሚገዛበት ገንዘብ የለውም ፣ ስለዚህ መሬት ወደ ግል ቢዞር በአንድ ብሄር እጅ ተመልሶ እንዲገባ ማድረግ ነው።” ብሎ ነበር። መለስ አንድ ብሄር የሚለው የፈረደበትን አማራ ነው። መለስ ባለፉት 23 አመታት ሲሰራ የነበረውም ካፒታሊስቶች በአብዛኛው ከራሱ ወገኖች ብቻ እንዲሆኑ ለማድረግ ነው። በአሁኑ ሰአት መሬትን ወደ ግል ማዞር የአገሪቱ ሰፋፊ መሬቶች በእነዚህ ካፒታሊስቶች እጅ እንዲወድቅ ማድረግ ነው። ወያኔ ዘረኛ መንግስት ባይሆን ኖሮ ችግር አይኖርብኝም ነበር። ዘረኛ መንግስት ደግሞ ፍታሃዊ በሆነ መንገድ መሬት ወደ ግል ያዞራል ብሎ ማለት ራስን ማሞኘት ነው።”

 

↧

የቀድሞው የጋምቤላ ፕሬዚዳንት ደቡብ ሱዳን ከሆቴል ውስጥ ታፈኑ “ወያኔ እጅ ገብተዋል”

$
0
0

downl44የጋምቤላ ክልልን ሲመሩ ቆይተው ባለመስማማት የኮበለሉት የቀድሞው የክልሉ ፕሬዚዳንት ደቡብ ሱዳን ከሆቴል ውስጥ ታፍነው መወሰዳቸው ተጠቆመ። ዜናው በገለልተኛ ወገን ባይገለጽም ኖርዌይ በስደት ከቤተሰቦቻቸው ጋር ይኖሩ የነበሩት አቶ ኦኬሎ አኳይ በኢህአዴግ በጥብቅ የሚፈለጉ ሰው ነበሩ።
በመለስ ዜናዊ ውሳኔ በአኙዋክ ተወላጆች ላይ በጅምላ የተከናወነውን ጭፍጨፋ አስመልከቶ ተቃውሞ በማሰማት የኮበለሉት አቶ ኦኬሎ ወደ ደቡብ ሱዳን ከማምራታቸው በፊት ኬንያ እንደነበሩ፣ ከኬንያ ወደ ደቡብ ሱዳን ለምን እንደተጓዙ የዜናው ምንጮች በይፋ ከመናገር ተቆጥበዋል። ስማቸው እንዲደበቅላቸው የጠየቁ የጋምቤላ አስተዳደር ባልደረባ ለጎልጉል የአካባቢው ዘጋቢ እንደተናገሩት አቶ ኦኬሎ ደቡብ ሱዳን ሆቴል በተቀመጡበት መታፈናቸውን አረጋግጠዋል።

“ወያኔ እጅ ገብቷል” ሲሉ ያከሉት እኚሁ ሰው “አቶ ኦኬሎ ብረት በማንሳት ወያኔን ለመታገል ከተነሱ ጋር ተቀላቅለዋል በሚል ስማቸው መመዝገቡንና ወደ ደቡብ ሱዳን ማቅናታቸው በመታወቁ ህወሃቶች እጅ ሊወድቁ ችለዋል” ብለዋል። ምንጩ ይህንን ይበሉ እንጂ አቶ ኦኬሎ አክዋይ ወደ ደቡብ ሱዳን ያቀኑበትን ምክንያት በርግጠኛነት ሃላፊነት ወስዶ የገለጸ ወገን አልተደመጠም። ኢህአዴግም ቢሆን የቀድሞውን ሹመኛ ስለመያዙ ይፋ ያደረገው ነገር የለም። ከደቡብ ሱዳን ቀውስ ጋር በተያያዘ የኑዌር ተወላጅ ከሆኑት ሬክ ማቻር ጦር ጋር በመሰለፍ የሳልቫ ኪርን ሃይል ሲወጉ ከተገደሉ ወታደሮች መካከል የኢህአዴግን ሰራዊት መለያ የለበሱ ኑዌሮች መገኘታቸው ውዝግብ አስነስቶ እንደነበር ያመለከቱት ምንጭ “ደቡብ ሱዳን እየወጋት ካለው ኢህአዴግ ጋር አብራ የቀድሞውን የጋምቤላ ርዕሰ መስተዳደር ከምድሯ ላይ እንዲታፈኑ መፍቀዷ ቅሬታ ያስነሳል” ብለዋል።

ከቤተሰባቸው ተነጥለው በስደት ከሚኖሩበት ኖርዌይ ወደ ደቡብ ሱዳን ያመሩት የቀድሞው የጋምቤላ ርዕሰ መስተዳድር ደቡብ ሱዳን በህወሃት ሙሉ ቁጥጥርና ፈቃድ የምትንቀሳቀስ አገር መሆኗን እያወቁ ወደዛ ማቅናታቸውን ባሥልጣኑ “ታላቅ ጥፋት” ብለውታል። ቤተሰቦቻቸውን ለማግኘት ያደረግነው ሙከራ አልተሳካም። በቅርቡ አቶ ኦሞት ኦባንግ መኮብለላቸውና በብዙዎች ዘንድ አውሮጳ እንዳሉ ቢነገርም በትክክል ያሉበት አገር በይፋ አለመታወቁን መዘገባችን ይታወሳል።
goolgule.com/

↧

ያልተሳካው የበድር ኢንተርናሽናል ሽምግልና

$
0
0
↧
↧

ሥጋታችን “አክራሪ” ሃይማኖተኝነት ሳይሆን አክራሪ “አይማኖተኝነት” ነው

$
0
0

አዲስ ጉዳይ መጽሔት
adebabayblog@gmail.com;

ይህንን ጽሑፍ ለመጀመር ትርጓሜ የሚያስፈልጋቸውን ሐሳቦች ብያኔ በመስጠት እነሣለኹ። ሃይማኖት እና አይማኖት። በጥሬ ትርጉሙ ከወሰድነው ሃይማኖት “አሚን፣ ማመን፣ እምነት፣ አምልኮ” ማለት እንደሆነ የግእዝ እና የአማርኛ ቀዳማውያት መዝገበ ቃላት ደራስያን ደስታ ተ/ወልድ እና ኪዳነ ወልድ ክፍሌ ይነግሩናል። ከዚያም አልፎ በዕለት ተዕለት ቋንቋችንና አነጋገራችን ካየነው ደግሞ እያንዳንዳችን የምንከተለውን እምነት እና ሃይማኖት በየስሙ እየጠራን “እገሌ የተሰኘው ሃይማኖት ተከታይ ነን” እንላለን።

“አይ” ደግሞ “የአሉታና የነቀፌታ ቃል ንኡስ አገባብ ሲኾን በቦታ፣ በኀላፊ፣ በትንቢት፣ ይገባል። ለምሳሌ “አይ ወዲያ፤ አይ በሉ” እንደሚባለው ነቀፌታን የሚያሳይ አገባብ ነው። “አይባልም፣ አይገባም፣ አይደለም፣ አይኾንም” የምንለውን ማስታወስ ነው።

“ያዲሳባ ሰው አይጦም አይበላ፤

አያርፍ አይሠራ” እንዲሉ አለቃ ደስታ ተ/ወልድ።

ከ“ሃይማኖት” አሉታን የሚያሳይ “አይማኖት” የሚል ቃል መፍጠሬን ይመለከቷል። ሃይማኖተኛ እንደሚለው እምነት አልባ፣ እግዜር የለሽ (Atheist) መሆን ብቻ ሳይሆን ለሃይማኖት ጥላቻ ያለውን ሰው “አይማኖተኛ” (Antitheist) ብንል ያስኬደናል። ቃሉ ለምን እንዳስፈለገን ወደ ጽሑፉ ገባ ስንል እንገነዘባለን። በፈጣሪ መኖር የማያምኑ (Atheist የሆኑ) ብዙ ሰዎች አሉ። ግን ሃይማኖትና አማኒውን ላይጠሉ ይችላሉ። ሃይማኖትን እና አማኙን ለሚጠሉ ግን አይማኖተኛ (አንቲቴይስት Antitheist) የሚለው ይህ ቅጽል ገላጭ ይሆናል። እናብዛው ካልን “አይማኖተኛ፣ አይማኖተኝነት” ልንለው እንችላለን።

++++

ሃይማኖት ሥር እንደ ሰደደባቸው እንደማንኛቸውም አገሮች ሁሉ ኢትዮጵያም ስለ ሃይማኖት፣ ሃይማኖት በሕብረተሰቡ የዕለት ተዕለት ኑሮ ላይ ስላለውና ሊኖረው ስለሚገባው ድርሻ እና ከፖለቲካ ጋር ስላለው ግንኙነት ሰፊ ውይይት ይደረግበታል። ውይይቱ አዲስ የተጀመረ ባይሆንም በዚህ ዘመን ያለው የጉዳዩ አያያዝ ከሌሎቹ ዘመናት በተለየ ሰፋና ጠለቀ ያለ ትርጉም እየተሰጠው ነው።

አገራችን አዲስ መንግሥት እና አዲስ ሕገ መንግሥት ከተመሠረተባት ካለፈው 20 ዓመት ወዲህ በአገሪቱ ስላሉት እምነቶች፣ ከፖለቲካው ጋር ስላላቸውና ሊኖራቸው ስለሚገባው ግንኙነት ሰፊ መንግሥታዊ እንቅስቃሴ እየተደረገ ነው። ይኸው መንግሥታዊ እንቅስቃሴ በሁሉም ዘንድ ያለው መረዳት አንድ ዓይነት ነው ማለት አይቻልም።

በሕገ መንግሥቱ ላይ መንግሥትና ሃይማኖት የተለያዩ ናቸው፤ መንግሥታዊ ሃይማኖት አይኖርም፤ መንግሥት በሃይማኖት ጉዳይ ጣልቃ አይገባም፤ ሃይማኖትም በመንግሥት ጉዳይ ጣልቃ አይገባም” ይላል። (ሕገ መንግሥት አንቀጽ 11)።

አንዱ በአንዱ ተግባር ውስጥ “ጣልቃ አለመግባት” ማለት ምን ማለት ለመሆኑ በራሱ መፍታታት ይኖርበታል። መንግሥት በሃይማኖት ላይ የተመሠረተ፣ አንድን እምነት የመንግሥት እምነት አድርጎ የሚቀበል አይሆንም፤ ሃይማኖትም በራሱ ተነሳሽነት “ሃይማኖታዊ መንግሥት ለመመስረት አይንቀሳቀስም”። በሳዑዲ አረቢያ ወይም በሌሎች የእስልምና አገሮች “የአገሪቱ ብሄራዊ እምነት እስልምና” ሆኖ እንደታወጀው በኢትዮጵያም “ብሔራዊ እምነት የሚባል” አይኖርም ብለን እንውሰድ። በተጨማሪም እምነቶች እንደ ፖለቲካ ፓርቲዎች የራሳቸውን መንግሥት ለማቋቋም አይሞክሩም። በእምነት ስም ለፖለቲካ ማራመጃነት ማንኛውንም ፓርቲ (ሃይማኖታዊ ፓርቲ) ማቋቋም  አይፈቀድም።

ሕገ መንግሥቱ “የሃይማኖት፣ እምነትና አመለካከት ነጻነት” ባለው ክፍል ውስጥ ደግሞ ተጨማሪ እምነት ነክ መብቶች ዘርዝሯል (አንቀጽ 27)። ሲጠቃለል፦ መንግሥት በዜጎች እምነት ነክ ጉዳይ ጥልቃ የማይገባ፣ ከሃይማኖት የራቀ፣ “ሴኩላር” መሆኑን ያስረግጣል።

የመንግሥት ሴኩላርነት፣ ሃይማኖትን እና መንግሥትን የመለየት ፍልስፍና ከራሳችን ያነቃነው ሳይሆን ከሌሎቹ አገራት የቀዳነው እንደመሆኑ ፍልስፍናው እና አስተምህሮው በሌሎቹም ዘንድ ለረዥም ጊዜ ሲሰለቅ የኖረ ነው። አልፍሬድ ስቴፓን የተባሉ ፀሐፊ ዲሞክራሲ በፖለቲካ፣ በመንግሥታትና በሃይማኖቶች መካከል ስላለው ግንኙነት ሲናገሩ በአራት ከፍለው ያስቀምጣሉ።

1ኛ. ሴኩላር የሆነ ይሁን እንጂ ለሃይማኖት ጥላቻ የሌለው መንግሥት አለ፤

2ኛ. ሴኩላር ያልሆነ (እምነት ነክ የሆነ) ይሁን እንጂ ለዲሞክራሲ ጥላቻ የሌለው መንግሥት አለ፤

3ኛ. ሴኩላሪዝም ያቆጠቆጠበት እና ሃይማኖት ምንም ተጽዕኖ የሌለበት ፖለቲካ አለ፤

4ኛ. ሴኩላር የሆነ ነገር ግን ለሃይማኖት ጥላቻ ያለውና በሃይማኖቶች እና በመንግሥት መካከል ጤናማ ያልሆነ ግንኙነት እንዲመሠረት የሚያደርግ አስተዳደርና ፖለቲካ አለ። (RAY TARAS. “POLAND’S TRANSITION TO A DEMOCRATIC REPUBLIC: The Taming of the Sacred?”. THE SECULAR and THE SACRED NATION, RELIGION AND POLITICS. (2005: p. 143)።

+++

ፈረንሳይ “ሴኩላር” የመንግሥት አስተዳደር የምትከተል ብትሆንምና ባለ ብዙ እምነት አገር ብትሆንም ለብዙ ዘመናት በአገሪቱ የቆየውን የካቶሊክ እምነት እና ባህል ግን ከአገሪቱ ማንነት ላይ ቀርፋ መጣል አትችልም። የሌሎችን እምነቶች ባህል ለማክበር የፈረንሳይ-ካቶሊክ እምነትና ባህል መጥፋት የለበትም። በታሪክ አጋጣሚ ካቶሊካዊነት ያገኘው ሥፍራ አሁን ባለው የእምነት-እኩልነት ምክንያት ሊኮስስ አይችልም።

ብዙ እምነት ካላቸው እና “ሴኩላር” አስተዳደር እንከተላለን ከሚሉት መካከል ሕንድን በተጨማሪ ብናነሣ አገሪቱ የተለያዩ እምነቶች አገር ብትሆንም ሁሉንም አስማምታ በአንድነት ማኖር የቻለችው ግን ገና ከ50 ዓመት ወዲህ ነው። ፓኪስታንን እና ሕንድና ያለያያቸው የርስበርስ ጦርነት የተደረገውና አንዷ ሀገር ሁለት ለመሆን የበቃችው በእምነት ልዩነት መስመር ነው። ፓኪስታን እስልምናን፣ ሕንድ ደግሞ ሒንዱ እምነትን በዋናነት በመያዝ። ሒንዱ ዋነኛው እምነት ቢሆንም አሁን ሕንድ ባላት ለእምነቶች ሁሉ እኩል ዕይታ ምክንያት ባለ ብዙ እምነት አገር ተብላ ትወሰዳለች። ሕገ መንግሥታቸውም ይህንን ያሳያል።

ሕንድ ሌሎች እምነቶችን ትቀበላለች ማለት የሒንዱ እምነት በአገሪቱ ላይ የነበረውን የቆየ አሻራ ታራክሳለች ማለት አይደለም። የአገሪቱ ባህላዊ ማንነት በሒንዱነት ቢበየን የታሪክ አጋጣሚ መሆኑ እሙን ነው። የቆየ እምነት ነውና ታሪካዊ ድርሻው ከፍ ማለቱ የማይጠረጠር ነው። ማንኛውም ሕንዳዊ የፈቀደውን እምነት መከተል ይችላል። ሁሉም እምነት ግን በሕንድ ታሪክ ላይ እኩል ድርሻ የለውም።

ከስፔን እስከ ቱርክ፣ ከፖላንድ እስከ አሜሪካ፣ ሃይማኖት ትልቅ ሥፍራ በሚይዝባቸው ነገር ግን መንግሥታቱ “ሴኩላር” ናቸው በሚባሉባቸው አገሮች በመንግሥታት እና በሃይማኖቶች መካከል እኩያነት፣ መከባበር፣ መተጋገስ እና ሕጋዊነት አለ። መጠናቸው ግን አንዱ ከአንዱ ይለያል።

+++

ባለፉት አርባ ዓመታት በአገራችን ያለው የፖለቲካ እና የሃይማኖት ግንኙነት ብንመለከት “ሴኩላር” መሆኑን ሁለቱም መንግሥታት ቢገልጹም “ምን ዓይነት ሴኩላር መንግሥት?” የሚለውን ግን የምንገነዘበው ከድርጊታቸውና ከተግባራቸው ብቻ ነው። በአልፍሬድ ስቴፓን  ሐሳቦች መነሻነት ከተመለከትናቸው መንግሥቶቻችን ሴኩላር ብቻ ሳይሆኑ ለሃይማኖት በጎ አመለካከት በሌለው ሴኩላር አስተሳሰብ ላይ የተገነባ ፍልስፍና  የሚከተሉ “አይማኖተኞች” መሆናቸውን መረዳት እንችላለን።

ይህ 40 ዓመት በትክክል ያሳየን አንድ ሐቅ ደግሞ አገራችንን ያጠፋው ይኸው አይማኖታዊ አመለካከት እንጂ ሃይማኖት አለመሆኑን ነው። በቀይ እና ነጭ ሽብር፣ በግራና በቀኝ አስተሳሰብ፣ በቋንቋና በዘር ፖለቲካ ወዘተ ተቆራቁሰን አገራችንን ከማጥፋታችን በስተቀር በሃይማኖት ሰበብ ድሆችና ኋላቀሮች አልሆንም። የእርበርስ ጦርነቶች ሕዝባችንን ያጎሳቆሉት ለአገራችን ችግር ዋነኛ ምክንያት ተደርጋ በምትፈረጀው በኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሰበብ አይደለም።

መንግሥት ሴኩላር መሆኑ ተገቢ ሊሆን ይችላል። ሃይማኖትን “ሴኩላር” ማድረግ ግን አይማኖተኝነትን በሃይማኖት ላይ መጫን ነው። ሰዎች በምርጫቸው እምነት አልባ መሆን መብታቸው ነው። በግድ እምነታቸውን ማስጣል እና ሃይማኖት ያላቸውን ሰዎች በጎ ባልሆነ አመለካከት መመዘን አይማኖተኝነት ነው። አክራሪነትን እቃወማለሁ። አይማኖታዊ አክራሪነትን ደግሞ የበለጠ እቃወማለሁ። አገራችንን ሲያጠፋ በደንብ አይቼዋለሁና። በተግባር የተገለጸ ሥጋታችን “አክራሪ ኦርቶዶክስ” ሃይማኖተኝነት ሳይሆን አክራሪ “አይማኖተኝነት” ነው።

ይቆየን – ያቆየን

 ይህ ጽሑፍ አዲስ አበባ ለሚታተመው የአዲስ ጌዳይ መጽሔት የተጻፈና በዚያም ላይ ለሕትመት የበቃ ነው።

↧

ይድረስ ለብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማቲያስ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት

$
0
0

 

ኤሎሄ! ቅዱስ! ኤልሻዳይ! አዶናይ! ያህዌ! ጸባዖት! ኢየሱስ! ክርስቶስ! አማኑኤል! በአብ በወልድ በመንፈስቅዱስ ሥም! አሜን!

አቤቱ አባት ሆይ ከእኛ ወገን ለአንተ እናት ሆናህ በእሷ በኩል በሥጋ ትዛመደን ዘንድ በመረጥካትና ስለብዙዎች ልቧ (አእምሮዋ) ሐዘንን (ነብዩ እንደተናገራት ፍላጻዎችን) ሁሉ ያስተናግድ ዘንድ ባጸናሀት፣ ቅድስት፣ ንፅህትና ዘላለማዊት ድንግል በሆነች እናትህ ማሪያም ሥም ማስተዋልን ትሰጠኝ ዘንድ እለምንሀለሁ! አሜን!

ብፁዕ አባታችን፡ ከዚህ በፊት የጻፍኩልዎት ደብዳቤ ይደረስዎት አይድረስዎት እርግጠኛ አይደለሁም፡፡ ግን እንደደረሰዎት እገምታለሁ እኔ ለአንባብያን በማህበራዊ ድህረገፆች እንዲነበብ ባደርገውም በደብዳቤው መልዕክት የተሳቡ አንዳንድ ሰዎች የእኔን ፍቃድ ጠይቀው በቀጥታ በፋክስ እንላኩልዎት ነግረውኛል፡፡ ጉዳዩ ዛሬ ደግሜ ከማነሳው ጋር ተመሳሳይ ነው፡፡ የበፊቱንም ደብዳቤ በድጋሜ አንባብያንም ይሁኑ እርሶም ማመሳከር ትችሉ ዘንድ ከዚሁ መልዕክት ጋር አያየዛለሁ፡፡ ከጉዳዩ መመሳሰል ባሻገር የወራቶቹም መመሳሰል ነገሩን በውል ላስተዋለው አስገራሚ ሊሆን ይችላል፡፡ ይህ ወራት በመላው የኦርቶዶክስ እምነት ተከታይ የጾምና ጸሎት እንዲሁም የንስሃ መቀበያ ወቅት እንደሆነ ልብ እንበል፡፡ ልክ የዛሬ ዓመት በዚሁ የጾም ወቅት ተከስቶ የነበረ (እንደውም የዛሬ ዓመት በጌታ ሕማም መታሰቢያ ሳምንት በነበረው የጾሙ ጊዜ ነበር) ጉዳይ ዛሬም ተከስቶ ሳየው ተገረምኩ እናም ተመሳሳይነት ያለው መልዕክት በድጋሜ ለእርሶና ለቤተክርስቲያኒቱ የውጭ ግንኙነጽ ኃላፊ እንዲሁም ለትዝብት ለሕዝብ ማስተላለፍ ፈለግሁ፡፡ ይህ ጉዳይ የመልአከ መንክራት (መምህር)ግርማ ወንድሙን አገልግሎት ይመለከታል፡፡

ሰሞኑን በአቡነ ገሪማ መምህሩን አስመልክቶ እንደተጻፉ የሚያሳዩ ሁለት ተቃራኒ መልዕክት ያለቸው ደብዳቤዎች ለሕዝብ በማሕበራዊ ገጾች በመድረሳቸው የዛሬ ዓመት ተከስቶ የነበረው አይነት ወዥምበር በሕዝብ ዘንድ ፈጥረው ታላቅ መነጋገሪያ ጉዳይ ሆነው ሰንብተዋል፡፡  የመጀመሪያው ደብዳቤ ከሰባት ወር በፊት እንደተጻፈ የሚያመለክት ሲሆን ደብዳቤው ለመምህሩ ዕውቅና የሰጠና አገልግሎታቸውንም ዓለም ዓቀፍ እንዲሆን የፈቀደ ሲሆን በቅርቡ በተመሳሳይ ፊርማና ማህተብ የወጣው ሌላ ደብዳቤ ደግሞ የበፊቱን በማጭበርበር የወጣ ብሎ የሚከስና የሚያወግዝ ነው፡፡

አሁን ጥያቄው የመምህሩ ችግር ወይንስ የእርሶና የፀሀፊው ሊቀ ጳጳስ ጽ/ቤት ችግር ነው የሚል ነው፡፡  መምህሩ በተጭበረበረ ማህተብና ፊርማ ሌላ ቦታ ያሰሩት ደብዳቤ ከሆነ በእርግጥም መምህሩ ተጠያቂ ይሆናሉ፡፡ ሆኖም ግን ከእርሶ ጽ/ቤት የወጡ ደብዳቤዎች ከሁኑ መምህሩን የሚያስጠይቃቸው አንዳች ጉዳይ አይታየኝም፡፡  ደብዳቤዎቹ ግን በተጭበረበረ ማህተብ የተጻፉ አይመስሉም፡፡ ፊርማውምና ቲተሩም  ቢሆን የሊቀ ጳጳሱ የራሳቸው እንደሆነ አናያለን፡፡ እነዚህ ተቃራኒ መልዕክት ያላቸው ደብዳቤዎች እንዴት በአንድ ሰው ፊርማ ወጡ ለሚለው የብዞዎች ግምት የጸ/ቤቱ እንደሆነ እንጂ የመምህሩ እንደሆነ አያሳይም፡፡ በተመሳሳይ የዛሬ ዓመት ከዚሁ ከእርሶ ጽ/ቤት የመምህሩን አገልግሎት ያወገዘውና ከእስጢፋኖስ ቤተክርስቲያን ያገደው ደብዳቤ ከፍተኛ የሆነ ግድፈትና  የጽ/ቤቱን ደረጃ የማይመጥን በልዩ ሴራ የደብዳቤን ይዘት፣ ሥርዓትና ቅደም ተከተል እንኳን በማያውቁ ግለሰቦች እንደተጻፈ አንበበናል፡፡ የአሁኖቹም ቢሆኑ ከቤተክርስቲያን መሠረታዊ መርሆ ወጣ ባሉ የጎደፉ ሕሊናዎች ሊሆኑ እንሚችሉ አንዳንድ ቃላቶችንና የሁኔታዎችን ሂደት እናያለን፡፡

የመጀመሪያው ደብዳቤ ስሕተት ነው ከተባለና ሁለተኛው እውነተኛ ሆኖ የመምህሩ አገልግሎት እውንም የሚወገዝ አይነት ከሆነ መምህሩ በይፋ የሚሰጡትን አገልግሎት በፖስታ በሚታሸግ ደብዳቤ ብቻ  ሊያውም ለማይመለከተው ሁሉ (አገልግሎትዎ ስህተት ነው ከተባለ የሚመለከተው በመጀመሪያ መምህሩን ነው) የጅምላ ደብዳቤ መጻፍ ስህተት ይመስለኛል፡፡ ይህ ደብዳቤ የተጻፈው በፊት ለተፈው ስህተት ለተባለው ምላሽ ብቻ ከሆነም የበፊቱ ለሚመለከተው ሁሉ ይላልና ይሄም ለሚመለከተው ሁሉ ቢባል ችግር የለውም ካልንና የመምህሩ አገልግሎት ግን ስህተት የለውም ተብሎ ከታመነ ሁለተኛው ደብዳቤ ከመጻፉ በፊት ቢያንስ የበፊቱ በምን አግባብ እንደሆነ ተጠንቶ መምህሩም ተጠይቀው ስህተቱ ይት ጋር እንዳለ ከተረጋገጠ በኋላ ሊሆን ይገባው ነበር፡፡ የመጀመሪያው ደብዳቤ ማንም ይጻፈው ማንም የመምህሩ አገልግሎት ግን እስከታመነበት ድረስ እንደተባለው የበፊቱ ከጽ/ቤቱ ያልወጣ ወይም አግባብ ባልሆነ ሁኔታ የወጣ ከሆነ ደብዳቤውን ማውገዝ ተገቢ ነው በምትኩ ግን የመምህሩን አገልግሎት የሚደግፍ ሌላ ትክክለኛ ደብዳቤ መስጠት የበጎ ሕሊና አሰራር ከመሆኑም ባሻገር አጋጣሚዎችን ለራሳቸው ፍላጎት ሊጠቀሙ የሚያስቡትን በር መዝጋት ነበር፡፡ ሆኖም አሁንም ቢሆን የሁለተኛው ደብዳቤ ይዘት የመምህሩን አገልግሎት አንቀበልምና ፍቃድ አለኝ ቢሏችኁ አተቀበሏቸው ጭምር ይመስላል፡፡ በዚህ የይዘት ትርጉም ደግሞ መምህሩ አሁን በይፋ  ተጻፈላቸውም አልተጻፈላቸውም በአለም አቀፍ ደረጃ እየሰጡት ያለው አስተምህሮትና  የፈውስ አገልግሎት በቤተክርስቲያኒቱ ሥምና በእርግጥም በቤተክርስቲያኒቱ አብያት ቅጥር ውስጥ እንደሆነ ስናስብ አገልግሎታቸውን በይፋ መንቀፍ ድፍረት በልታጣ ነበር፡፡ በይዘትና ደረጀ ሚዛን ሲመዘኑ ግን ሁለቱም ደብዳቤዎች የተንገዳገዱና ነገር እንዳለባቸው እንረዳለን፡፡ መምህሩ ግን የሚያውቁት ነገር ያለ አይመስልም፡፡

እኔ የመምህሩን አስተምህሮትም ሆነ የፈውስ አገልግሎት በአትኩሮትና በመገረም በአካልም በጉባዔያቸው በመገኘት  ጭምር የምከታተል ሰው ነኝ፡፡ የመምህሩ አስተምህሮት ዛሬ እንደ አሸን የፈሉት ተራ ሰባክያን አስተምህሮት ከጩኸት የዘለለ ሕይወትን ለመለወጥ አቅም የሌለው ሳይሆን በትኩረት ለአዳመጠው ጥልቅ የሆነ ከልዑል አምላክ ዘንድ በምትፈስ ጥበብ/ፍልስፍና የተዋበ አእምሮና ሕሊና እውነትን እንዲጋፈጧት የሚያስገድድ ነው፡፡ በተግባር የሚያደርጉት የልዑል እግዚአብሔርን ኃይል በገሀድ ማሳየትና የጠላታችንን ሴራ ማጋለጥ የአገልግሎታቸው ምስክሮች ናቸው፡፡  ይህ ነበርና ጥንታዊው የሐዋርያት ክርስትና፡፡ ዛሬ ግን ጰውሎስ እንህ አለ፣ እንዲህ አደረገ፤ ዮሐንስ እንዲህ አለ እንዲህ አደረገ ከሚለን በቀር እነዚያ ታላላቅ ተአምራትን በጌታ ሥም የሚያደርጉትን የሚያደርግ ለመኖሩ ማረጋገጫ እንኳን አጥተናል፡፡ በአንጻሩ ቀሚሳቸውን አስረዝመው እጅጌያቸውን አስፍተው በከተማ በመንገማለል በአለባበሳቸውና በአነጋገራቸው ሊከብዱብን የሚሞክሩ ብዙዎች ናቸው፡፡ በእንዲህም አይነት ሳይገደቡ በቤተክርስቲያንና በሕዝብ ገንዘብ የራሳቸውን ዓለም የሚቀጩት ይሄ ለቤተክርስቲያኒቱ አስተዳደርና ሥርዓት አደገኛ ኪሳራ ሆነዋል፡፡   ይህን እውነት ሕሊናችን ሊክደው አይችልም፡፡ በጎ ነገርንና ለልዑለአማላክ መገዛትን በቀጥታ የሚናገሩት ግን መምህሩን ጨምሮ በበጎ አይን አይታዩም፡፡ መምህሩ በልዑል አማላክና በቅዱሳኑ ሥም ከክፉ መናፍስት በመናፍስቱ ከሚመጡ ደዌያትንና የኑሮ ምስቅልቅሎች የተጨነቁትን መታደጋቸው አደገኛ ጠንቋይ አስማተኛ አሰኝቷቸዋል፡፡ እርግጥ አስማተኛ መባላቸውን እኔም ብሆን ቅር የምሰኝበት አይደለም፡፡  የመምህሩ አስማት ግን ሌሎች ክፉዎቹ የሚጠሩት ሳይሆን፣ ኃያሉና ጉልበትን ሁሉ የሚያንበረክከው የክርስቶስና ስሙ በስማቸው የታተመው የቅዱሳኑ ግን ሥም እንደሆነ በአየናችን አይተናል እኛም እንድንሞክረው አድርገው ብዙዎች በሥሙ ክፉውን መንፈስና ጠንቆቹን እተዋጉት ይገኛሉ፡፡ ይህ አስማተ መለኮት መተተኞቹ የሚቋቋሙት አይደለም፡፡ መምህሩ  ጠንቋይና መተተኛ ላለመሆናቸው እኛ ምስክሮች ነን፡፡ ችግሩ ቤተክርስቲያንን የወረሯት መተተኛ ደብተራዎችና ጠንቋዮች ሥራቸው እየከሸፈባቸው ስለሆነ የመምህሩን ከምድረገጽ መጥፋት አጥብቀው ይፈልጉታል፡፡ መጻሕፍ ይጠቅሳሉ፣ ሴራ ይሸርባሉ አቅማቸው የፈቀደውን ሁሉ ይሞክራሉ፡፡ ግን የልዑል አማላክን ክንድ ሊያጥፍ የሚችል ማን ነው! ሌሎች የተደነባበሩትን ለማደናገር ይሞክራሉ፡፡ አልቀረባቸውም ክፉና አመንዝራ ትውልድ ምልክትን ይሻል በማለት የመምህሩን የማዳን ፀጋ ሊያጣጥሉ ይሞክራሉ፡፡ ጌታም ሆነ ሐዋሪያቱ ምልክትን እንድንመረምር አስጠነቀቁን እንጂ አይተን እንዳናምን አልተናገሩም፡፡ ጌታንም ሆነ ሐዋሪያትን የተቀበሏቸው ብዙዎች በአዩት ተዓምር እንጂ በትምህርታቸው እንዳልሆነ እንረዳለን፡፡ ደግሞ በተግባር የማይገለጥ እምነት የለመድንው ተረት አይነት እንጂ እንዴት እውነት ሊሆን ይችላል፡፡ በሥሙ ለሚያምኑት ሁሉን ያደርጉ ዘንድ ሥልጣንን እንደሰጣቸው ሲታወስ ምንም ማድረግ የማንችል የመተተኞችታ የክፉ መናፍስት መጫወቻ የሆንን ግን ክርስቲያነ ነን ብለን የሚናምን እስኪ ለክርስትናችን ምልክቱ ምንድነው?

እውነት እንደ መምህር ግረማ ብዙዎችን ከዘመናት ጭንቅ የገላገለ ማን ነው? ብዙዎችንስ እምነታቸውን እንዲያውቁ ያደረገ ማን ነው? ብዙዎቻችን እኮ ክርስትናው ከተረት ያለፈ ትርጉም አልሰጠን ብሎ ነበር! የየትኛው ሰባኪ አስተምሮት ነው ብዙዎችን ከሌላ እምነት ወደክርስትናው የመለሰ? ሰብከት ተብዬዎች ብዙዎች ጦርነትን መለያየትን የሚያውጁ አይደሉም እንዴ! ማነው እንደ እኚህ መምህር ዘር ሳይል ሀይማኖት የተሰጠውን ፀጋ ለሁሉም በእኩል ሊያበረክት የወደደ፡፡ ዘረኝነትና ጎጠኝነትን የሚያስፋፉ አይደሉም እንዴ ዛሬ ቤተክርስቲያኒቱን የወረሯት፡፡ ማን ነው እን እኚህ መምህር ለቤተክርስቲያን ልማት ተሳታፊ የሆነ፡፡ በሚሊየን የሚቆጠር ገንዘብ ለቤተክርስቲያን ዛሬ እያስገባ ያለው በእሳቸው ትምህርት አይደለም እንዴ? ማንው ይህንን ሁሉ ገቢ ለቤተክርስቲያን እያስገባ በነጻ አንዳች ደሞዝ እንኳን ሳይቀበል የሚያገለግል፡፡ በየክብረ በዓል በአሰልቺ ሁኔታ የሚሰበሰብን ገነዘብ  ካላካፈላችሁን፣ አበል ካልከፈላችሁን የሚሉ ሰባክያንና መዘምራን አይደሉም እንዴ ዛሬ የሞሉን፡፡ የጌታን ትዕዛዝ በለመጠበቃቸው ግን መካኖች እንደሆኑ አይረዱም፡፡ በነጻ የተቀበላችሁትን በነጻ ስጡ ይላልና፡፡ እንደመምህሩ ያለ ጸጋ ሊኖረው የሚፈልግ ገዘብን ወዶ ሊሆንለት አይችልም፡፡

አባ በእናንተስ መካከል (በጳጳሳቱ ማለቴ ነው) ስለመምህሩ ለምን ይሄን ያህል መለያየት ተፈጠረ? ጥሩና አስተዋይ መሆናቸውና በሕዝብ ዘንድ ተወዳጅ የሆኑት ብዙዎቹ ጳጳሳት መምህሩን በትክክልም ሲደግፉ በጉባዔያቸውም እየተገኙ ሕዝቡን ሲባርኩ አይተናል፡፡ ደብዳቤዎቹ ማን እንደጻፋቸውም ስለማናውቅ ተጭበረበሩ እንበል፡፡ ግን እኮ አይናችን እያየ ጆሮአችንም እየሰማ ከእናነተ እኮ የመምህሩን አገልግሎት አለም አቀፋዊነት በአንደበታቸው ነው የተናገሩት፡፡ ይሄም ፊልም ነው ሊሉ ይችላሉ፡፡ እኛ ግን በአካል ተገኝተን የያየንና የሰማን ምስክሮች ነን፡፡ ደግሞ እግዚአብሔርን ሥራ ለመሥራት የማንንም ፍቃድና እውቅና ማግኘት ያለባቸው አይመስለኝም፡፡ ጥንታዊው የሐዋሪያትም ጉዞ በካህናትና በነገስታት ፍቃድ ሳይሆን ከአምላካቸው የተሰጠውን ትዕዛዝ ብቻ ከመፈጸም ነበርና፡፡

አባ አሁንም አላለሁ ሕሊና የልዑል አምላክ እንደራሴ ነው፡፡ እውነት ግን ከሕሊናም በላይ ስለሆነች በልዑል አምላክ የምትመሰል ናት፡፡ እግዚአብሔር እውነት ነውና፡፡ በሕሊናችን ካልበደልን እውነትን ብንስታት እንኳን የእውነት ባለቤት እግዚአብሔር እውነትን እንድናውቃት ያደርጋል፡፡ ሁሌም አነሳዋለሁ በሕሊናው ምንም በደል የሌለበት ግን እውነትን ባለማወቁ የክርስቲያኖች አሳዳጅ የነበረውን ሳውል (ቅዱስ ጳውሎስን)፡፡ በተቃራኒው እውነትን አውቆ ግን ሕሊናውን በሰላሳ ብር የሸጠውን ይሁዳንም እናስተውል፡፡ እውነትን ለመቀበል እያወቁ እምቢ ያሉትን የአይሁድ ካህናትንም፡፡ ጳውሎስ ስለሕሊናው ምርጥ የክርስቶስ ምርጥ ሊሆን ተመረጠ እውነት በተገለጠችለት ጊዜ ሕሊናው እውነትን ሊክድ የሚችል አልነበረምና፡፡

አባ አሁንም አላለሁ ሁላችሁም የሕሊናችሁን ንፅሕና እንድትመረምሩ፡፡ በስልጣንና በከፍተኛ ማዕረግ መቀመጥ እንደ አይሁድ ካህናት ክርስቶስን የሚያስክዳችሁ ምቾት አይሁንባችሁ፡፡ ስለ ሕዝብና ስለትውልድ መጨነቅን ልመዱ፡፡ የድህነትን መንገድ ለማሳየት መነገድ የጠፋበትን ታች ወርዳችሁ ምሩት፡፡ ክርስትናው ወግና ልማድ ብቻ ሆኖ ሕዝብ በክፉ ኃይል እንደወደቀ አስተውሉ፡፡ ከልዑል እግዚአብሔር ክብር ሕዝብ ለክፉ መንፈስ እንደተገዛም እዩ፡፡ ጠንቋዮችና ደብተሮች ከፍተኛ ክብር አላቸው፡፡ በቤተክርስቲያኒቱም ከፍተኛ ስልጣን ላይ እንዳሉ እናውቃለን፡፡ ሲያስፈራሩን ቆይተዋል! ዛሬ ግን ሊቋቋሙት የማችሉትን እኛም ታጥቀናል፡፡ የዛሬ ዓማት በእስጢፋኖስ ቤተክርስቲያን የነበረው የመምህሩ የማስተማሪያና የፈውስ አገልገሎት መስጫ መድረክ ከነቅዱሳን ሥዕላቶቹ ድምጥማጡ ሲጠፋ ከጠንቋዩች፣ ቃሊቻዎች፣ ሌሎችም ጣዖት አማላኪዎች እየተሰበሰቡ የሚመጡ የጣዖት ማመለኪያ እቃዎች የሚጣሉባት አንዲት ትንሽ ክፍል ግን አንዳች አልተነካችም፡፡ ሰይጣን ነብረቱን ምን ያህል እንደሚጠብቅ ብዙዎቻችን አየን፡፡ ዛሬም ድረስ በዚያው ጊቢ ያቺ ክፍል ብቻዋን አለች፡፡ እግዚአብሔርን ለማወቅ ባልፈለጉት መጠን የማይገባውን ያደርጉ ዘንድ ለማይረባ አእምሮ አሳልፎ ሰጣቸው  ያለው ፈላስፋው እውነት ነው፡፡ አስደንጋጭም ነው! አንዴ ለማይረባ አእምሮ ከተጣልን በምን ማሰብ እንችላለን፡፡ ጌታን በአጋንንት አለቃ አጋንንትን ያወጣል ባሉት ጊዜ የተናገረው አሳዛኝ መልዕክትም በአእምሮዬ መጣ፡፡ “እኔ በአጋንንት አለቃ አጋንንትን የማወጣ ከሆነ ልጆቻችሁ በምን ያወጧቸዋል” አለ፡፡ አዎ በጌታ ሥም ማመን ካልቻልን በምን ክፉውን ልንቋቋመው እንችላለ፡፡

ብዙ ጉዳዩች በአእምሮዬ አሉ እዚሁ ላይ ላቁም ግን ለሁለተኛ ጊዜ እለምንዎታለሁ፡፡ ሥለ ሕሊና ፍርድ ራስዎ በይፋ ይናገሩ፡፡ ስለመምህሩም ስለሌላውም የቤተክርስቲያኒቱ ጉዳይ፡፡ እኛም ስለሕሊናችን አገልጋዮች እንሆናለን፡፡ አምላክም እውነትን እንከተላት ዘንድ እንደ ቅዱስ ጰውሎስ የአይናችንን ቅርፊት ያስወገድልናል! በእውነትም ተጉዘን መንግስቱን እንወርሳለን፡፡

ቅዱስ እግዚአብሔር አእምሮአችንን ይክፈት!

አሜን

የታላቋ ቀን ልጅ መጋቢት 21 2006 ዓ. ም

↧

የማሕበረ ቅዱሳን የመጨረሻዎቹ ቀናት –ከተመስገን ደሳለኝ

$
0
0

“ማሕበረ-ወያኔ” 

mahbere-kidusan-300x168በኮሎኔል መንግስቱ ኃይለማርያም የሚመራው መንግስት ከናቅፋ እስከ ጉና ተራራ ያሉ ምሽጎቻቸውን ከሰማይ በጦር አይሮፕላን፣ ከምድር እሳት በሚያዘንቡ ቢ.ኤሞችና መድፎች ሳያቋርጥ ደበድብም፤ በሀገሪቱ ሰሜናዊ አካባቢ ከቀን ወደ ቀን ግዛታቸውን እያሰፉ የተጠናከሩት ‹‹ወንበዴዎች›› ራስ ምታት ሆነውበታል፡፡ የኤርትራ ‹‹ነጻ አውጪ›› ቤዝ-አምባው በተወሰነ መልኩም ቢሆን ለጥቃት የመጋለጥ እድሉ አናሳ በሆነው የሳህል በረሃ በመሆኑ አብዛኛው የአመራር አባል መሸሸጊያው አድርጎታል፡፡

 

በተመሳሳይ መልኩ በትግራይ አካባቢ የሚንቀሳቀሱት የወያኔ መሪዎች ምሽጋቸው እንደ ሳህል ምቹ ባለመሆኑ፤ በርካታ ክፉ ቀናትን ያሳለፉት በተራራማ አካባቢዎች በሚገኙ የኦርቶዶክስ ክርስትና እምነት ገዳማት ውስጥ ተደብቀው እንደሆነና ከቦታ ቦታ መዘዋወር ሲፈልጉም የመነኮሳቱን አልባሳት ይጠቀሙ እንደነበረ በትግሉ ዙሪያ የተዘጋጁ ድርሳናት ያወሳሉ፡፡ በተለይም ታጋይ መለስ ዜናዊ፣ አባይ ፀሀዬ፣ ግደይ ዘርአፅዮን፣ ስዩም መስፍን፣ ስብሐት ነጋን…. የመሳሰሉ የአመራር አባላት የገዳማቱ ቤተኛ ነበሩ፡፡ ከዚሁ ጋ ተያይዞ የሚነገርም አንድ ታሪክ አለ፤ የመንግስት ፀጥታ ሰራተኞች ሁለት የ‹‹ወንበዴ›› መሪዎች በትግራይ በሚገኝ አንድ ገዳም ውስጥ ከመነኮሳቱ ጋር ተመሳስለው መሸሸጋቸው መረጃ ይደርሳቸውና በጥቂት ሰዓታት ውስጥ እስከ አፍንጫቸው የታጠቁ ወታደሮችን በመላክ ዙሪያ ከበባ ያደርጋሉ፡፡ ይሁንና መደበቂያ በመስጠት የረዷቸው መነኮሳት ሁለቱን ታጋዮች ‹‹ወይባ›› በመባል የሚታወቀውን ረጅሙን ቀሚሳቸውን አልብሰው እና ቆብ አስደፍተው ከአካባቢው በማሸሽ ይታደጉዋቸዋል፡፡ የታሪኩ ባለቤት መለስ ዜናዊ እና አባይ ፀሀዬ ነበሩ፡፡ በርግጥ እነዚህ የ‹‹ወንበዴ›› መሪዎች ‹በእንዲህ አይነቱ ከመርፌ አይን እጅግ በጠበበ ዕድል ህይወታችን ከሞት መንጋጋ ተርፎ ኮለኔል መንግሥቱን በጓሮ በር ወደ ዜምባብዌ ሸኝተን በትረ-መንግሥቱን ለመጨበጥና ለሃያ ምናምን ዓመታት ኢትዮጵያን ታህል ታላቅ ሀገር አንቀጥቅጠን ለመግዛት እንበቃለን› የሚል ጠንካራ እምነትና የእርግጠኝነት ስሜት በወቅቱ ነበራቸው ብሎ ማሰብ ለእነርሱም ቢሆን እጅግ አዳጋች ይመስለኛል፤ የሆነው ግን ይህ ነበር፡፡

 

 ‹‹ማሕበረ-ቅዱሳን››

 

መለስ ዜናዊና ጓዶቹ በለስ ቀንቷቸው ባልጠበቁት ፍጥነት የመንግሥት ‹‹ጠንካራ ይዞታ›› የሚባሉ ከተሞችን ሳይቀር እየተቆጣጠሩ ወደ አዲስ አበባ የሚያደርጉትን ግስጋሴ ሲያፋጥኑ፤ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ደግሞ በመንግሥቱ ኃይለማርያም ሰብሳቢበት፣ በደህንነት ሠራተኞች እና የኢሠፓ ካድሬዎች ገፋፊነት ትምህርታቸውን አቋርጠው ለወታደራዊ ስልጠና ደቡብ ኢትዮጵያ ወደሚገኘው ብላቴና የጦር ማሰልጠኛ ከተቱ፤ ዩኒቨርሲቲውም ተዘጋ፡፡

 

…ከመላው ዘማቾቹ አስራ ሁለት የሚሆኑ ተማሪዎች ተሰባስበው ሲያበቁ፣ በየቀኑ ካምፓቸው አቅራቢያ ወደሚገኘው ‹ሚካኤል ቤተ-ክርስቲያን› በመሄድ፣ ከመዓቱ ይታደጋቸው ዘንድ ፈጣሪያቸውን በፀሎት መማፀን የህይወታቸው አካል አደረጉት፤ ከቀናት በኋላም በአንዱ ዕለት አንድም ለመታሰቢያና ለበረከት፣ ሁለትም ስብስቡ ሳይበተን ወደፊት እንዲቀጥል በሚል ዕሳቤ ‹ማህበረ ሚካኤል› ብለው የሰየሙትን የፅዋ ማህበር መሠረቱ፡፡ …ይሁንና ከመካከላቸው አንዳቸውም እንኳ በ1977 ዓ.ም በ‹ፓዊ መተከል› ዞን የተደረገውን ‹የመልሶ ማቋቋም› ፕሮግራም እንዲያመቻቹ በዘመቱ ተማሪዎች ከተመሠረተውና ከተለያዩ የፅዋ ማህበራት ጋር በመዋሀድ የዛሬውን ‹ማህበረ-ቅዱሳን› እንደሚፈጥሩ መገመት የሚችሉበት የነብይነት ፀጋ አልነበራቸውም፤ የሆነው ግን እንዲያ ነበር፡፡

 

 

ኃይማኖትን ጠቅልሎ የመያዝ ዕቅድ

 

በትጥቅ ትግሉ ወቅት የህወሓት አመራር ገዳማትን ለመሸሸጊያነት ብቻ ሳይሆን ለእርካብ መወጣጫነትም ጭምር ተጠቅሞባቸዋል፡፡ ከድርጅቱ መስራቾች አንዱ የነበረው አረጋዊ በርሄ ለዶክትሬት ዲግሪ ማሟያ ‹‹A Political History of the Tigray People’s Liberation Front (1975-1991): Revolt, Ideology and Mobilisation in Ethiopi›› በሚል ርዕስ ጽፎት፤ ኋላም ወደ መጽሐፍ በቀየረው የጥናት ጽሁፉ ላይ፣ ‹‹የቤተ-ክርስቲያኗን ሥልጣን (በትግራይ የነበረውን) ለማድቀቅ ሲባል በስብሀት ነጋ የሚመራ የስለላ ቡድን ተቋቋመ፡፡ ይህ ቡድንም ደብረ-ዳሞን ጨምሮ በትግራይ ውስጥ ባሉ ገዳማት አባላቱን መነኮሳት በማስመሰል፣ የገዳማቱን እንቅስቃሴ በህወሓት ፍላጎት ስር የማስገዛት ስራ ሰርቷል›› ሲል በገፅ 317 ላይ ገልጿል፡፡ ድርጅቱ ሙሉ በሙሉ ሐይማኖትን ጠቅልሎ ለመያዝ የተነሳበትን ገፊ-ምክንያትም እንዲህ በማለት አብራርቶታል፡-

 

 

‹‹ቤተ-ክርስቲያኗ ተከታዮቿን፣ ለነበረው የኢትዮጵያ መንግስት እንዲገዙ ከማስተማር በዘለለ የብሔራዊ ንቃት (ማንነት) ማስተማሪያም ነበረች፡፡ …ለህወሓት እንቅስቃሴ እንቅፋት እንደነበረች ግልፅ ነው፡፡ ስለዚህም ቤተ-ክርስቲያኒቱን በህወሓት ዓላማ ስር ለማሳደር ፍላጎት ነበር፤ በዚህ የተነሳም የእርሷን ተፅእኖ ለማግለል ጥልቅ እርምጃዎች ተወስደዋል፡፡›› (ገፅ 315-316)   ዶ/ር አረጋዊ ‹‹ጥልቅ እርምጃዎች›› ብሎ ከጠቀሳቸው መካከል አንደኛው ‹‹ለአጥቢያ ቀሳውስቱ ኮንፍረንስ በማዘጋጀት፣ በትግራይ ውስጥ ያሉትን ቤተ-ክርስቲያናት ለብቻ ነጥሎ ህወሓት በሚያራምደው የትግራይ ብሔርተኝነት ስር ማካተት›› እንደነበረ በዚሁ መጽሐፍ ጠቅሷል፡፡ ይሁንና አስገምጋሚ መብረቅ የወረደብን ያህል የምንደነግጠው፣ ዶ/ሩ ከዚሁ ጋ አያይዞ ‹‹የተጨቆነው የትግራይ ብሔርተኝነት የተነሳሳውም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ-ክርስቲያንን ተፅእኖ ለመገዳደር ነው›› በማለት መመስከሩን ስናነብ ነው፡፡ የአረጋዊ መረጃ የሰሚ-ሰሚ ወይም በቢሆን ሃሳብ የተቀኘ አይደለም፤ ይልቁንም ራሱም በመሪነትና ሃሳብ በማዋጣት ከተሳተፈበት ከድርጅቱ የፖለቲካ ፕሮግራም የተቀዳ እንጂ፡፡

 

የሆነው ሆኖ ህወሓት ከ1970-72 ዓ.ም ድረስ ባሰለጠናቸው ካድሬ ‹‹ካህናት›› አማካኝነት ‹‹ነፃ በወጡ›› መሬቶች ላይ ራሱን የቻለ የቤተ-ክህነት አስተዳደር (ከሲኖዶሱ የተገነጠለ) መመስረቱ ይታወሳል፡፡ ድርጅቱ ለእነዚህ ቤተ-ክርስቲያናት መተዳደሪያ ደንብ ከመቅረፅ አልፎ ዓላማውንም እንደ አስርቱ ትዕዛዛት በፍፁም ልባቸው የተቀበሉ ‹‹መንፈሳዊ ክንፍ›› አድርጓቸው እንደነበረ፣ አረጋዊ በርሄ ተንትኖ አስረድቷል፡፡ እንዲህ አይነቱ ሰርጎ ገብነት በእስልምናም ላይ መተግበሩ አይዘነጋም፡፡ በተለይም የእምነቱ ተከታዮች በሚበዙበት አካባቢዎች ወላጆቻቸው ሙስሊም የሆኑ ታጋዮችን እየመረጠ እና ከክርስቲያን ቤተሰብ የወጡ ካድሬዎችንም ሀሰተኛ የሙስሊም ስም እየሰጠ ‹የትግሉ ዓላማ እስልምናን ማስፋፋት› እንደሆነ በመግለፅ የፕሮፓጋንዳ ስራ ይሰራ ነበር፡፡ በዚህ ስልቱ በተወሰነ ደረጃም ቢሆን የአንዳንድ ዓረብ ሀገራትን ቀልብ ማግኘት ችሏል፡፡ ይህ ደግሞ ከዓረቦች በገፍ ዕርዳታ ያጎረፈለት ሲሆን፣ ወደ መሀል ሀገር የሚያደርገውን ጉዞም አፋጥኖለታል፡፡

 

ከመንግስት ለውጥ በኋላም ሁለቱን ሐይማኖቶች የተቆጣጠረው በታጋይ ‹‹ካህናት›› እና ‹‹ሼሆች›› ለመሆኑ በርካታ ማሳያዎች አሉ፡፡ ዛሬም በኦርቶዶክስ ክርስትና እምነት የበላይ በሆነው ጠቅላይ ቤተ-ክህነት ውስጥ ከሚገኙት አስራ ስምንት መምሪያዎች፣ አስራ ስድስቱ በህወሓት ሰዎች የመያዛቸው ኩነት ስልቱ በተሳካ ሁኔታ መተግበሩን ያስረግጣል፡፡ በተለይ ዋነኛው ሰው አቡነ ማቲያስ ሲኖዶሱን ብቻ በሚመለከት ጉዳይ ላይ ጭምር ውሳኔ ከመተላለፉ በፊት ‹‹የመንግስት ባለሥልጣናትን ላማክር›› ሲሉ በተደጋጋሚ መደመጣቸው እና አንዳንድ ጳጳሳት ተቃውሞ በሰነዘሩባቸው ቁጥር በአፃፋው ‹‹መንግስት ያግዘኛል ብዬ ነው እዚህ መንበር ላይ የተቀመጥኩት፤ ባያግዘኝ ሥልጣኑን አልቀበልም ነበር›› በማለት በግላጭ ሲመልሱ መስተዋላቸው ለስርዓቱ ጣልቃ-ገብነት እንደማሳያ ሊቆጠር ይችላል፡፡ ከዚህ ቀደም ለሶስት ወር የቋሚ ሲኖዶሱ አባል ሆነው የሰሩ አንድ ጳጳስም ‹‹ሁልጊዜም ቋሚ ሲኖዶሱ ሲሰበሰብ እርሳቸው (ፓትርያርኩ) ‹መንግስት እንዲህ አለ›፣ ‹መንግስት ሳይፈቅድ›… የሚል ንግግር ይጠቀማሉ›› በማለት ለፋክት አስተያየት ሰጥተዋል (በነገራችን ላይ ፓትርያርኩ የመዘንጋት፣ ለውሳኔ የመቸገር፣ እንቅልፍ የማብዛትና መሰል ችግሮች ስራቸውን እያስተጓጎሉባቸው እንደሆነ ይነገራል፤ ራሳቸውም ‹‹ሲጨንቀኝ እተኛለሁ፤ ስተኛ ደግሞ እረሰዋለሁ›› በማለት ችግሩን አምነው ተቀብለዋል)

 

በእስልምና እምነት ውስጥም የመንግስት ጣልቃ-ገብነት ከቀድሞውም መጅሊስ የባሰ እንደሆነ በርካታ መዕምናን የሚያውቁት እውነታ ነው፡፡ ይህ መጅሊስ የሚዘወረው እንደተለመደው በምክትል ፕሬዚዳንቶች ሲሆን፤ ይች አይነቷ ጨዋታ ደግሞ ህወሓት ጥርሱን የነቀለበት ስለመሆኑ ነጋሪ አያሻም፡፡ ምክትል ፕሬዚዳንቱ ሼህ ከድር ለ17 ዓመታት የትግራይ ክልል መጅሊስና የሸሪአ ፍ/ቤቱን ደርበው በመያዝ መእምናኑን ቀጥቅጠው ሲገዙ ከመቆየታቸውም በላይ ታጋይ እንደነበሩ በኩራት ለመናገር የሚደፍሩ እንደሆነ የቅርብ ሰዎቻቸው ይመሰክራሉ፡፡ በአናቱም ከታማኝ የመረጃ ምንጭ ባይረጋገጥም የመጅሊሱ ፕሬዚዳንት ሼህ ኪያር መሀመድ ከእኚሁ ‹‹ታጋይ›› ምክትላቸው ጋር በአንዳንድ ጉዳዮች መስማማት ባለመቻላቸው እና ‹‹መንግስት የሚያዘውን ሁሉ ለመስራት ለምን እንገደዳለን?›› የሚል ተቃውሞ እስከማሰማት በመድረሳቸው በቅርቡ ከኃላፊነታቸው ሊነሱ እንደሚችሉ ተወርቷል፡፡

 

 ኢህአዴግ እና ‹‹መንፈሳዊ›› ገበያው

 

ግንባሩ የእምነት ተቋማትን በአብዮታዊ ዲሞክራሲ አስተሳሰብ ጠርንፎ መያዝን እንደ ዋነኛ ዓላማ አድርጎ የመንቀሳቀሱ መግፍኤን ከሶስት ጉዳዮች አንፃር በአዲስ መስመር ለመተንተን እሞክራለሁ፡-

የመጀመሪያው ቤተ-ክህነት በነገስታቶቹ ዘመን የነበራትን ፖለቲካዊ ተሰሚነት (ምንም እንኳን ራሱ ኢህአዴግም በአፋዊነት ከማውገዝ ቸል ባይልም) ለቅቡልነት መጠቀሚያ የማድረግ ፍላጎቱ ነው፡፡ በገቢር እንደታየውም በኃይል በተቆጣጠራቸውም ሆነ ካድሬዎቹ ሊደርሱባቸው በማይችሉ የገጠር ቀበሌዎች ተቀባይነት ለማግኘት ማህበራዊ አክብሮት ባላቸው ሼሆች፣ ቀሳውስት፣ ዲያቆናት… ሲቀሰቅስ ተደጋጋሚ ጊዜ ተስተውሏል፡፡ እንዲሁም የእስልምና እምነት በታሪክ ያሳለፈውን አገዛዛዊ ጭቆናንም ሆነ የደርጉን ሁሉንም ሐይማኖት ማግለልን በማጎን ለፕሮፓጋንዳ ተጠቅሞበታል (በወቅቱ የድርጅቱ አመራር አባል የነበረው አቶ ገብሩ አስራት፣ እንደ ሼሆች በመልበስና በመጠምጠም ከፍተኛ አስተዋፆ ማበርከቱን ብዙሀኑ ታጋዮች አይዘነጉትም) በዚህ ዘመንም በቤተ-እምነቶች ካድሬ-ጳጳሳትንና ካድሬ-n ሼሆችን አሰርጎ የማስገባቱ ምስጢር ይኸው ነው፡፡

 

 

በሁለተኛነት እንደምክንያት ሊጠቀስ የሚችለው የታገለለትን ዘውግ ተኮር ፖለቲካ ያለአንዳች ተግዳሮት ማሳለጥን ታሳቢ ማድረጉ ይመስለኛል፡፡ ምክንያቱም የሁሉም ሐይማኖቶች ‹‹የሰው ልጅ በሙሉ የአንድ አምላክ ፍጡሮች ናቸው›› በሚል አስተምህሮ የሚመሩ ከመሆናቸው አኳያ፣ በዘውግ ከፋፍሎ ማስተዳደርን ቀላል አያደርገውምና ነው፡፡ ስለዚህም መፍትሔው አክራሪ ብሔርተኛ ‹‹መንፈሳውያን›› በየእምነት ተቋማቱ እንዲፈለፈሉ እና ከፍተኛውን የሥልጣን እርከን መቆጣጠር እንዲችሉ በማብቃት ላይ የተመሰረተ ብቻ መሆኑን የህወሓት መሪዎች ያውቃሉ፡፡ ይህ ‹‹እውቀታቸው››ም ይመስለኛል ሀገራዊ ስሜት የሌላቸው፣ በችሎታ ማነስ እና በስነ-ምግባር ጉድለት የሚታወቁ፤ እንዲሁም በእምነቱ ተከታዮች ዘንድ ቅቡል ያልሆኑ ሰዎች ቦታውን እንዲይዙ እስከማድረግ ያደረሳቸው፡፡

 

የራሳቸው የስለላ መዋቅርም በጥቅምት 2 ቀን 1995 ዓ.ም ‹‹ለዋናው መ/ቤት፣ አዲስ አበባ፤ ከ-ል.ዮ፡ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ አቡነ ጳውሎስን ጉዳይ ይመለከታል›› በሚል ርዕስ ለደህንነቱ ዋና መስሪያ ቤት በላከው ጥናታዊ ዘገባ ላይ እውነታውን እንዲህ ሲል ገልፆታል፡- ‹‹…ለፓትርያርኩ ወዳጅነት አላቸው የሚባሉ ሊቃነ ጳጳሳት ከሦስትና አራት ብዙም ያልበለጡ ናቸው፡፡ ፓትርያርኩ ምንም ዓይነት ተቀባይነትና ከበሬታ ያጡ በመሆናቸው ህልውናቸውን የአንዳንድ መሪዎችን ስም በመጥራትና እንደማስፈራሪያ በመጠቀም ላይ የተንጠላጠለ ሆኗል››፡፡ ከዚህ ሪፖርት በኋላም እንኳ ለማስተካከል አለመሞከሩ መከራከሪያውን አምነን እንድንቀበል ያስገድደናል፡፡

 

አገዛዙ መንፈሳዊ ተቋማትን ጠቅልሎ ለመያዝ ለሚያደርገው እንቅስቃሴ በሶስተኛነት ሊጠቀስ የሚችለው ምክንያት፣ ምንም እንኳ ‹‹ተሳክቷል›› ሊባል ባይቻልም፤ በስነ-ምግባር መታነፅ፣ በሀገር አንድነት ማመን፣ ለሕዝብ ጥቅም መቆም፣ የትኛውንም ህገ-ወጥነት ‹ለምን› ብሎ መጠየቅና መሰል መንፈሳዊ አስተምህሮዎችን መርሁ አድርጎ የሚነሳ ትውልድ እንዳይፈጠር መከላከልን ታሳቢ በማድረግ እየሰራ ያለውን ሴራ ነው ብዬ አስባለሁ፡፡ ምክንያቱም የስርዓቱ ሰዎች በዚህ መልኩ የሚቀረፅ ትውልድን ዛሬ ባነበሩት አይነት የጭቆና ቀንበር ለተራዘሙ ዓመታት መግዛት ከባድ እንደሆነ ለመረዳት አይሳናቸውምና ነው፡፡ ከዚሁ ጋር አንስተን ማለፍ ያለብን ጭብጥ፤ መቃብር ከሚቆፈርለት የኢትዮጵያዊ ብሔርተኝነት ጋር የሚያያዝ ነው፤ የሐይማኖቱና የማዕከላዊ መንግስቱ የቅድመ-አብዮቱ ጋብቻ (በምንም አይነት መከራከሪያ ትክክለኛነቱን ልንሟገትለት ባንችልም)፣ ቤተ-ክርስቲያኗ ለኢትዮጵያዊ ብሔርተኝነቱ የታሪክ ብያኔ ከፍተኛ አስተዋፆ ማድረጓን አያስክደንም፡፡ ይህም ‹የሐይማኖቱን ተቋም የብሔርተኝነቱ ወካይ ሆኖ እንዲታሰብ ይገፋዋል› ብሎ ለሚያምነው ህወሓት፣ ሐይማኖቱ ተቋማዊ ነፃነት እንዳይኖረው የሚቻለውን ሁሉ ሲያደርግ፤ ሐይማኖቱን በማዳከም የብሔርተኝነት መንፈሱንም ማላላት ይቻላል ከሚል መነሾ ነው ብሎ መደምደም ተምኔታዊ አያስብልም፡፡

 

 ገደል አፋፍ የቆመው ማሕበረ ቅዱሳን…

 

ስርዓቱ የሐይማኖት ተቋማትንና መንፈሳዊ መሪዎቹን ለመቆጣጠር ገፊ-ምክንያቶች ሆነውታል ብዬ ከላይ ለማብራራት የሞከርኳቸውን ሶስት ምክንያቶች ሙሉ ለሙሉ መተግበርን አስቸጋሪ ያደረገበት፣ ቀጥታ በምዕምናኑ የተመሰረቱ ማሕበራት መሆናቸውን መገመት ይቻላል፡፡ ለማስረጃም ያህል ከኦርቶዶክስ ክርስትና-ማሕበረ ቅዱሳን፤ ከእስልምና ያለፉትን ሁለት ዓመታት የእምነቱ ተከታዮች ወካይ ሆኖ የተመረጠው ኮሚቴ አባላት መንግስትንም ሆነ መጅሊሱን በመገዳደር ያደረጉትን አበርክቶ መጥቀስ ይቻላል፡፡ ይሁንና የሙስሊሙን ተወካዮች በገፍ ሰብስቦ እስር ቤት ካጎረ በኋላ፣ ከሲኖዶሱም ሆነ መሰል ማሕበራት ጠንካራ እንደሆነ የሚነገርለትን ማሕበረ ቅዱሳንን ዋነኛ ኢላማው አድርጎ ለመደፍጠጥ የቆረጠ ይመስላል፡፡ የማሕበሩ አባላት በዓለማዊ እውቀት የተራቀቁ፣ በሀገር አንድነት በፍፁም የማይደራደሩ፣ በጥቅመኝነት የማይደለሉ… የመሆናቸው ጉዳይ አገዛዙ ከኃይል አማራጭ የቀለለ መፍትሔ የለም ብሎ እንዲያምን አድርጎታል ብዬ እገምታለሁ፡፡

 

በርግጥ በአቶ መለስ ዜናዊ ይዘጋጅ እንደነበረ ከህልፈቱ በኋላ በተነገረለት የኢህአዴግ የንድፈ ሃሳብ መጽሔት ‹‹አዲስ ራዕይ›› ከተወሰኑ ዓመታት በፊት አብዛኛውን ጊዜ ‹‹የከሰሩ ፖለቲከኞች ‹ኢትዮጵያ የክርስቲያን ደሴት ናት፣ አንድ ሐይማኖት አንድ ሀገር› እና ‹ሙስሊሙ ማሕበረሰብ ቀደም ሲል ሲደርስበት የነበረውን በደል በማራገብና በመቀስቀስ፤ ከዚህም አልፎ ተገቢነት የሌላቸው አዳዲስ ጥያቄዎችን በማቅረብ ለማነሳሳትና ለማተረማመስ ሲሰሩ ማየት የተለመደ ሆኗል›› በማለት ከሚያቀርበው የሾላ-በድፍን ፍረጃ ዘልሎ ብዙም መንፈሳዊ ማሕበራትን በስም ጠቅሶ ሲያወግዝ አይሰማም ነበር፡፡ ዛሬ ዛሬ ግን ማንኛውንም ሐይማኖታዊ የመብት ጥያቄን ‹‹ወሃቢያም ይሁን ማሕበረ ቅዱሳን…›› በማለት ማውገዙ የተለመደ ሆኗል፡፡ ከውግዘትም ተሻግሮ ጥያቄያቸውን በሕጋዊ መንገድ ወደ አደባባይ ያወጡትን የሙስሊሙን ተወካዮች ሰብስቦ አስሯል፤ በተለያየ ጊዜ የተደረጉ ሰላማዊ ተቃውሞዎችንም በማስታከክ በበርካታ የእምነቱ ተከታዮች ላይ ግድያና ስቀየትን ጨምሮ ብዙ ግፍ በመፈፀም ጉዳዩን በጠብ-መንጃ ብቻ የሚፈታ አድርጎ ካወሳሰበው ሰነባብቷል፡፡

 

‹‹ቀጣዩ የኢህአዴግ ኢላማ ማሕበረ ቅዱሳን ይሆን?›› በሚል ርዕስ ከስድስት ወር በፊት በዚሁ መጽሔት ላይ ለማተት እንደሞከርኩት ሁሉ፤ ከላይ በተዘረዘሩ የፖለቲካ አጀንዳዎች እና በሚቀጥለው ዓመት የሚካሄደውን አገር አቀፍ ምርጫ በለመደው የማጭበርበር መንገድ አሸንፎ ያለኮሽታ የሥልጣን እድሜውን ለማራዘም ዓለማዊም ሆነ መንፈሳዊ ነፃ ተቋማት እንዳይኖሩ በይፋ ኢ-ሕገ መንግስታዊ ድርጊቶችን እየፈፀመ ያለው የእነ አባይ-በረከት መንግስት፣ በአሁኑ ወቅት ሙሉ ትኩረቱን ማሕበረ ቅዱሳን ላይ ማድረጉን መረጃዎች ይጠቁማሉ፡፡

ይህንን አፈና ለማሳካትም ፓትርያርኩ አቡነ ማትያስ በፍፁም ልባቸው ከመተባበር ለአፍታም እንደማያመነቱ በርካታ ማሳያዎች አሉ፡፡

ለምሳሌ ያህልም አንዱን በአዲስ መስመር ላቅርብ፡-

 

ከወራት በፊት የአዲስ አበባ ሀገረ-ስብከት አስተዳደርን ወደ ዘመናዊነት ለማሻገር ሲኖዶሱ ጥናት ተደርጎ እንዲቀርብለት ውሳኔ አሳልፎ ነበር፡፡ እናም ጥናቱ ተጠናቆ ይፋ መደረጉን ተከትሎ ከአንዳንድ የደብር አስተዳዳሪዎች ብርቱ ተቃውሞ ስለገጠመው፣ በሀገረ-ስብከቱ ሥራ-አስኪያጅ አቡነ እስጢፋኖስ አማካኝነት በጠቅላይ ቤተ-ክህነት አዳራሽ ከሁሉም አድባራትና ገዳማት የተወጣጡ 2700 ሰዎች የሚሳተፉበትና አስራ አራት ቀን የሚፈጅ የውይይት ፕሮግራም ይዘጋጃል፡፡ ይሁንና ውይይቱ በተጀመረ በሁለተኛው ቀን ጠዋት ፓትርያርኩ፣ ከአቡነ እስጢፋኖስ ጋር በስልክ ከሞላ ጎደል እንደሚከተለው መወዛገባቸውን ሰምቻለሁ፡-

 

‹‹ጥናቱን የሚሰሩት ባለሙያዎች ናቸው ብለውኝ አልነበረም ወይ?››

‹‹አዎ! ታዲያስ ባለሙያዎች ናቸው የሰሩት፡፡››

‹‹አይደለም! የማሕበረ ቅዱሳን አባላት ናቸው፤ እርስዎ አታለውኛል!››

‹‹የጥናት ኮሚቴው አባላት በቤተ-ክርስቲያን ልጅነታቸውና በየአጥቢያው ባላቸው ተሳትፎ ተጠርተው የመጡ ሙያቸውን ‹አስራት› ያደረጉ ናቸው፡፡››

‹‹በፍፁም! ጥናቱ የማሕበረ ቅዱሳን ነው!››

‹‹ቅዱስ አባታችን ቢሆንስ? ከጠቀመን ችግሩ ምንድን ነው?››

‹‹በቃ! ውይይቱ ከመንግስት ይቋረጥ ተብሏል፡፡››

‹‹ለምን ይቋረጣል?››

‹‹የጥናቱ ተቃዋሚዎች ረብሻ ያስነሳሉና የፀጥታ ስጋት አለ፡፡››

‹‹ለምንድን ነው ረብሻ የሚያስነሱት? ከፈለጉ መጥተው መሳተፍ ይችላሉ፤ እኛ እየተወያየን አይደለም እንዴ! ተቃውሞ ያለው መጥቶ ሃሳቡን ይግለፅ እንጂ ማቋረጥ እንዴት መፍትሄ ይሆናል? ደግሞስ ሲኖዶሱ አይደለም ወይ ‹ሰነዱ ወደታች ወርዶ ይተችበት› ብሎ የወሰነው?››

‹‹የለም! ይቁም ተብሏል፤ ይቁም!››

‹‹እንግዲያውስ የከለከለው አካል ራሱ መጥቶ ይንገረን፡፡››

 

…የስልክ ምልልሱ ከተጠናቀቀ ከሰዓታት በኋላ አንድ ባለሥልጣን አቡነ እስጢፋኖስ ቢሮ ድረስ መጥቶ ትእዛዙን ያስተላለፈው እርሱ እንደሆነ ገልፆ ውይይቱ እንዲቋረጥ አሳሰባቸው፤ እርሳቸውም ‹‹እናቋርጣለን፤ ነገር ግን እናንተ ‹የፀጥታ ስጋት አለ› ብላችሁ በደብዳቤ ኃላፊነቱን ውሰዱ፡፡ እኛም ለካህናቱም ሆነ ለመዕምናኑ ሁኔታውን ዘርዝረን እንገልፃለን›› የሚል ምላሽ ሰጥተው ይሸኙታል፡፡ ከዚህ በኋላ ነው እንግዲህ ለጊዜው ግልፅ ባልሆነ አንድ ምክንያት መንግስት ‹‹ይቋረጥ›› የሚለውን ማስፈራሪያ ሊያነሳ የቻለው፡፡ ኩነቱ ግን ፓትርያርኩ ማሕበሩን በጥርጣሬ ማየታቸውንና አገዛዙ ለሚወስድበት ማንኛውም አይነት እርምጃ ተባባሪ መሆናቸውን የሚያሳይ ይመስለኛል፡፡

 

ሌላው መንግስትና ፓትርያርኩ፣ ማሕበረ ቅዱሳንን ለማፍረስ በሰምና ወርቅነት እየሰሩ መሆናቸውን የሚያመላክተው የዛሬ ሳምንት በጠቅላይ ቤተ-ክህነት የማሕበሩ ተቃዋሚዎች ያደረጉትን ውይይትና የአቋም መግለጫ ስናስተውል ነው፡፡ ለመጽሔቱ ዝግጅት ክፍል የደረሰው በድምፅ የተቀረፀ የውይይቱ ሙሉ ክፍል እንደሚያስረዳው፣ ተሰብሳቢዎቹ ማሕበሩን በተመለከተ ባወጡት የአቋም መግለጫ የሚከተሉትን ነጥቦች ዘርዝረዋል፡- ‹‹የዋነኛ አመራሮቹ የባንክ አካውንት ይመርመር፣ የማሕበሩ ሒሳብ መንግስት በሚመድበው የውጪ ኦዲተር ይመርመር፣ ቋሚና ተንቀሳቃሽ ንብረቶቹ (ከቀረጥ ነፃ ያስገባቸው ቀላልና ከባድ መኪናዎቹ ሳይቀሩ) ወደ ቤተ-ክህነት ይግቡ፣ የንግድ ተቋማቱ (ትምህርት ቤት፣ ሬስቶራንቶቹን፣ ንዋየ ቅድሳት ማምረቻና ማከፋፈያውን) ያስረክብ፣ ከምዕምናን በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ የሚቀበለው አስራት እየፈረጠመበት ስለሆነ እንዳይቀበል ይከልከል፣ የግቢ ጉባኤ (በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት) እርሱ በሚቀርፀው እንዳይወሰዱ መስራት፣ ተጠሪነቱ ከዋና ሥራ-አስኪያጁ ተነስቶ፣ በሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ ስር አንዱ ንዑስ ክፍል ይሁን…›› የሚሉና የመሳሰሉት ይገኙበታል፡፡

 

ከዚህ ሴራ ጀርባ ፓትርያርኩና መንግስት በትብብር መቆማቸውን የሚያሳየው በተቀረፀው ድምፅ ላይ፣ የውይይቱ መሪ አዳራሹን መጠቀም የቻሉት በአቡኑ መልካም ፍቃድ እንደሆነና እርሳቸው በዛሬው ውይይት ያልተገኙት የሕዳሴው ግድብ ምክር ቤት አባል በመሆናቸው ግዮን ሆቴል ስብሰባ ስላለባቸው መሆኑን ከመግለፅም በዘለለ፤ ‹‹ቅዱስ አባታችን በዚህ የተቃውሞ ምክንያት ከሥራ የሚባረር የለም አይዟችሁ አትፍሩ ብለውናል›› በማለት ሲናገሩ መደመጣቸው ነው፡፡ በተጨማሪም ‹‹ከዚህ ግቢ አቅም ኖሮት የሚያስወጣን የለም፤ ካስወጡን ግን መንግስታችን ስለሚተባበረን (ቸር ስለሆነ) ከእርሱ ሌላ መሬት ተቀብለን የራሳችንን ቤተ-ክርስቲያን እናቋቁማለን›› እና ‹‹የኦርቶዶክስ እምነት አገልጋዮች የሚል ማሕበር እንመሰርታለን›› እስከማለት መድረሳቸው ከአገዛዙ ጋር ያላቸውን የጠበቀ ቁርኝት ያመላክታል፡፡ በነገራችን ላይ በስብሰባው እንዲሳተፉ ከተጠሩት ከመቶ ስልሳ ዘጠኙ አድባራትና ገዳማት፣ እንዲሁም ከ10 ሺህ በላይ ሠራተኞቻቸው መካከል የተገኙት የስምንት አድባራት አስተዳዳሪዎችና 150 ሠራተኞች ብቻ እንደነበሩ ከመረጃ ምንጮቼ አረጋግጫለሁ፡፡

 

 

በሌላ በኩል ደግሞ በተለይም በፌዴራል ጉዳዮች ሚኒስቴር ምኒስትር ዶ/ር ሽፈራው ተክለማሪያም አዝማችነት ማሕበሩ ላይ የደቦ ዘመቻ ከተከፈተ ሰነባብቷል፡፡ በተከታታይ በ‹‹ጥናት›› ስም የሚወጡ ወረቀቶች ማሕበሩን ከአክራሪነትም አሻግረው ‹‹የግንቦት ሰባት መንፈሳዊ ክንፍ›› ሲሉ ይወነጅሉታል፡፡ በጥቅሉ የእነዚህ ‹‹ጥናት›› ተብዬዎች መደምደሚያ ‹‹ማሕበሩ የትምክተኞች ምሽግ ነው፣ አክራሪነት አለበት፣ አመራሩና የሕትመት ውጤቶቹ የፖለቲካ አዝማሚያ ይታይባቸዋል፣ በቤተ-ክርስቲያን አስተዳደር ጣልቃ ይገባል፣ ሕዝቡ በመንግስት ላይ አመኔታ እንዳይኖረው ይሰራል፣ በውጭ ፅንፈኛ የፖለቲካ ኃይሎች ይዘወራል›› የሚሉ ናቸው፡፡ የማሕበሩ የአመራር አባላት እንዲህ አይነቱን ውንጀላ በተመለከተ በተለያየ ጊዜ ከአቶ በረከት ስምኦን እስከ ዶ/ር ሽፈራው ተክለማሪያም፤ ከአዲስ አበባ የፀጥታ ኃላፊዎች እስከ ጠቅላይ ሚንስትሩ የደህንነት አማካሪ ፀጋዬ በርሄ ድረስ ያሉ ባለሥልጣናትን በቢሮአቸው ተገኝተው ውንጀላው ማስረጃ የማይቀርበበት የሀሰት እንደሆነ ቢያስረዱም መፍትሄ እንዳላገኙ ምንጮች ተናግረዋል፡፡ በግልባጩ በመንግስት ተቋማት ያሉ የፋክት መረጃ አቀባዮች፣ በግንቦት ወር ከሚካሄደው የሲኖዶሱ መደበኛ ጉባኤ በፊት፣ ከሃያ የሚበልጡ የማህበሩ አመራርን ከሽብርተኝነት ጋር በማያያዝ ለመክሰስ እና ማሕበሩንም እንደተለመደው በዶክመንተሪ ፊልም ለመወንጀል ዝግጅት መደረጉን ተናግረዋል፡፡ ከሶስት ሳምንት በፊት በአቡነ ገብርኤል ሰብሳቢነት የሚመራው የሐይማኖቶች ምክር ቤት ስብሰባውን ካጠናቀቀ በኋላ ዶ/ር ሽፈራው አቡኑን ቃል-በቃል የጠየቃቸው ጥያቄም ይህንን መረጃ የሚያጠናክር ነው፡-

 

‹‹በማሕበረ ቅዱሳን አመራር ውስጥ ከሃያ በላይ የተቃዋሚ ፓርቲ አባላት አሉ››

‹‹ለዚህ ምንድን ነው ማስረጃህ? አቅርበውና እስቲ እንየው?››

‹‹ሀገር ውስጥ ካሉ ፅንፈኛ ጋዜጠኞች በተጨማሪ በስደት የሚገኙና በሽብር ተግባር የተሰማሩ ጋዜጠኞች በአመራርነት አሉበት (የሁለት ሰዎችን ስም ጠቅሷል)››

‹‹እኛ እስከምናውቀው ማሕበሩ ከእንዲህ አይነት ተግባር የራቀ ነው፤ እናንተ ማስረጃ አለን ካላችሁ ደግሞ አቅርቡልንና እንየው፤ ከዚህ ውጪ ይህንን አይነት ክስ አንቀበልም፡፡››

 

በአናቱም ከወራት በፊት የስርዓቱ የንድፈ ሃሳብ መጽሔት የማሕበሩን ስም ሳይጠቅስ በደፈናው የወነጀለበትን እና ‹‹ለምን?›› ብለው የሚጠይቁ ጳጳሳትን በሚከተለው አገላለፅ ማሸማቀቁን ስናስታውስ የማሕበሩ ዕጣ-ፈንታ በመጨረሻዎቹ ቀናት ላይ መቆሙን ያስረግጥልናል፡፡

 

‹‹በኦርቶዶክስ ቤተ-ክርስቲያን ውስጥ ትርምስና ብጥብጥ ለመፍጠር፤ በኦርቶዶክሶችና ሌሎች ሐይማኖቶች መካከል ግጭት ለመቀስቀስ የሚሞክሩት የደርግና የተለያዩ ትምክህተኛ ኃይሎች ቅሪቶች ናቸው፡፡ እነዚህ የትምክህት ኃይሎችና አንዳንድ የእምነቱ አባቶች በጋራ ሐይማኖትን በፖለቲካ ዓላማ ዙሪያ መጠቀሚያ አድርገው እየሰሩ ለመሆናቸው ከ97 ምርጫ በኋላ እንዳንድ በአሜሪካ የሚገኙ ጳጳሳት ቅንጅት በጠራው ሰልፍ ላይ የሐይማኖት አባትነት ካባቸውን እንደለበሱ ከመሰለፍ አልፈው አስተባባሪ ሆነው መታየታቸው በቂ ማረጋገጫ ነው፡፡›› (አዲስ ራዕይ ሐምሌ-ነሐሴ 2005)

 

የሆነው ሆኖ ከፍረጃውና ከእስራቱ በተጨማሪ ማሕበሩን ለማዳከም በዋናነት በአገዛዙ የተነደፉት እቅዶች ማሕበሩ መሰረቱን የጣለበት የግቢ ጉባኤን ከመከልከልና ንብረቶቹን ከመውረስ ጋር የሚያያዙ ናቸው (ከላይ የተጠቀሰው የአቋም መግለጫም ለማሕበሩ የደም-ስር የሆኑትን እነዚህን ሁለት ጉዳዮች ትኩረት እንደሰጣቸው ልብ ይሏል)

 

ስቅለትን-ለተቃውሞ

 

ኢህአዴግ ወደ ስልጣነ-መንበሩ ከመጣ ሦስተኛ ዓመት ላይ ‹‹የአብዮታዊ ዴሞክራሲ ግቦችና ቀጣይ እርምጃዎች›› በሚል ርዕስ ለካድሬዎቹ በበተነው ድርሳን (በሟቹ አቶ መለስ ዜናዊ የተዘጋጀ ነው ተብሎ ይገመታል)፤ ይህን አሁን የተነጋገርንበትን ሐይማኖታዊ ተቋማትን በሚያቅዳቸው የስልጣን ማራዘሚያ አማራጮች ስለመጠቀም ካወሳ በኋላ ተቋማቱን ለስርዓቱ ፖሊሲዎች እንዲታመኑ ማድረጉ ዋነኛ እንደሆነ ያሰምርበታል፡፡ ይህ የማይቻል ከሆነ ደግሞ፣ እስከ ከፍተኞቹ መንፈሳዊያን መምህራን ድረስ ዘልቆ በመግባት ሐይማኖቶቹን መምራት የአብዮታዊ ዴሞክራሲ ግብ መሆን እንዳለበት ያው ሰነድ በግልፅ ቋንቋ ይናገራል፡፡ እንግዲህ ከመጅሊሱ እስከ ማሕበረ ቅዱሳን ያየነው መንግስታዊ አፈና የዚህን ሃያ ዓመት የሞላው የተፃፈ ሀሳብ መተግበርን ነው፡፡

 

ግና፣ ከዚህ ቀደም በተፃፈ ነውረኛ ሀሳብ ትግበራ ፊት ከሁለት አስርት በላይ ህልውናውን ለማቆየት የተጋው ማሕበረ ቅዱሳን፣ ከላይ በሚገባ በጠቀስኳቸው አሳማኝ መረጃዎች እና ተጨባጭ ሁነቶች በተከታታይ መከሰት መጨረሻው ምዕራፍ ላይ እንደደረሰ ተመልክተናል፡፡ በዚህ አስቸጋሪ ወቅት ደግሞ፤ መነሳት የሚኖርበት መሰረታዊ ጥያቄ፣ እንዴት ይህን ማሕበር ወደ ቀጣዩ ትውልድ ማሻገር ይቻላል? የሚለው ሲሆን፤ ምላሾቹም ሁለት ናቸው፡፡ የመጀመሪያው የማሕበሩ አመራሮችና አባላት እስከዚህች ቀን እያደረጉ ያለው የውስጥ ለውስጥ የእርምት እንቅስቃሴን ይመለከታል፡፡ በሐይማኖቱ ተቋማት በኩል ለዓመታት ሲሞከር የቆየው ይኸኛው አማራጭ፣ እንደ አስተዋልነው ማሕበሩን ሞት አፋፍ ላይ ከመድረስ ሊታደገው አልቻለም፡፡ ስለዚህም፣ ወደ ሁለተኛውና ዋነኛ የመፍትሔ አማራጭ መሻገር ግድ የሚል ይመስለኛል፡፡ ከዚህ ቀደም በተመሳሳይ ርዕሰ-ጉዳይ ላይ ስፅፍ ለማስረዳት እንደሞከርኩት፤ የማሕበሩ አመራሮች፣  አባላት እና ደጋፊዎች ወደ አደባባይ በመውጣት፤ ማሕበራቸውን ብቻ ሳይሆን ህልውናቸውንና ህያውነታቸውን የመሰረቱበትን ሐይማኖት ለማውደም የሚተጋውን ስርዓት በሰላማዊ አመፅ መናድ ብቸኛው የዚህ አስቸጋሪ ጊዜ መሻገሪያ መንገድ ነው፡፡ በዋናነት የተማሩ ከተሜ ወጣቶችን፣ በአለማዊም ሆነ በትምህርተ-ሐይማኖቱ የማይታሙ ዜጎችን የያዘው ይህ ማሕበር፤ ከህዝበ ሙስሊሙ ‹‹ድምፃችን ይሰማ›› የአደባባይ ተቃውሞ ስኬቶችና ሂደቶች በመማር፤ ፊቱ በተገተረው ኢህአዴግ ላይ በሕጋዊና ሰላማዊ እምቢተኝነት ከማመጽ የተሻለ አማራጭ እንደማይኖረው የሚረዳ ይመስለኛል፡፡

 

‹‹ችግሮች ሁሉ የየራሳቸው በጎ ገፆች አሏቸው›› እንዲሉ፤ ማሕበሩ የደረሰበት ይህ ፈታኝ ጊዜን ተከትለው የሚመጡ ሁለት ወቅቶች አሉ፡፡ የመጀመሪያው፣ በቀጣዩ ወር የሚካሄደው የስቅለት በዓል ነው፡፡ የሐይማኖቱ ተከታዮች በሙሉ በየቤተ-ክርስቲያናቱ የሚውሉበት ይህ በዓል፣ አገዛዙ እጁን ከማህበሩ ላይ እንዲያነሳ ለመጠየቅ የተመቸ ቀን ስለመሆኑ ማስታወስ አባላቱን አሳንሶ መገመት እንደማይሆን ተስፋ አደርጋለሁ፡፡ ሁለተኛውና በእጅጉ የተሻለ ነው ብዬ የማስበው ጊዜ ደግሞ ቀጣዩ የ2007 ምርጫን ነው፡፡ ለየትኞቹም የህገ-መንግስቱ ሀሳቦች አልያም የሞራል ዕሴቶች የማይገዛው ኢህአዴግ፣ በሐይማኖቱ ላይም ሆነ በማሕበሩ ላይ የዘረጋውን የረከሰ እጅ እንዲያነሳ ያለው ብቸኛ አማራጭ ሕዝባዊ አመፅ መሆኑ ላይ እስከተማመንን ድረስ፣ ከዓመታዊ የንግስ በዓላት ጀምሮ ያሉ መድረኮችን በዕቅድ ለመጠቀም የዝግጅቱ ጊዜ ዛሬ ነው፡፡ ይህ አይነቱ የተቃውሞ እንቅስቃሴም፣ ካነሳነው ርዕሰ-ጉዳይ አኳያ የማሕበሩን መኖር የሚሹ ሁሉ ቀጣዩን የምርጫ ወቅት ለማስገደጃነት የመጠቀም ተሞክሮዎቻቸውን ተፈላጊው ብቃት ላይ እንደሚያደርሰው አምናለሁ፡፡ ጥቂት ሊባሉ የማይችሉ አባላቱ፣ የምርጫውን ተጨባጭ ዕድል መንግስታዊ ተቋማት በማሽመድመድ ጭምር እንዴት ስርዓቱን ወደመቃብሩ ማሻገር እንደሚያውቁ ስንገነዘብ፤ ቀሪው ጉዳይ ‹‹ሐይማኖታችሁን ተከላከሉ›› ብለው ላስተማሩት ቅዱሳን መጻሕፍትና ለሰማያዊው መንግስት የመታመን ብቻ እንደሚሆን እንረዳለን፡፡

↧
Viewing all 15006 articles
Browse latest View live