Quantcast
Channel: Ethiopian News | ዘ-ሐበሻ | Latest News Provider | News For All
Viewing all 15006 articles
Browse latest View live

የአንዱአለም አራጌ ቀን በዋሺንግቶን ዲሲ ከተማ

↧

↧

[የሚኒሶታውን ደብረሰላም መድሃኔዓለም ቤ/ክ ጉዳይ ለምትከታተሉ ሁሉ] ቅጥፈታቸው ሲጋለጥ

$
0
0

debereselam Minnesota
ለሰላምና ለአንድነት የቆሙ ምዕመናን 3/24/2014
ቅጥፈታቸው ሲጋለጥ

ቤተክርስቲያናችን ተክሷል ስለዚህም ጠበቃ ቀጥረናል እያሉ ሲያወናብዱ የከረሙት አንዳንድ ሕገ-ወጥ የቦርድ አባላት ባለፈው ቅዳሜ 3/22/2014 መድኃኔዓለም በቤቱ አጋልጧቸዋል። ምንም አይነት ሕጋዊ የቅጥር ውል ስምምነት ፊርማ ከቤተክርስቲያኑ ጋር ሳይኖራት የቤተክርስቲያናችን እና የቦርዱ ጠበቃ ነኝ ስትል የከረመችው ግለሰብ በህዝብ እና በጠበቆች ፊት ቤተክርስቲያኑን ለመወከል ምንም አይነት የጽሑፍ ስምምነት እንዳልፈረመች ተናግራለች። በቤክርስቲያናችን የውስጥ ጉዳይ ጣልቃ በመግባት በሕጋዊው የቤተክርስቲያናችን ሊቀመንበር ላይ ከስልጣንህ ወርደሃል ከቦርዱም ተባረሃል በማለት ደብዳቤ በመጻፍ እንዲሁም ፖሊስ በሃሰት በመጥራት የቤተክርስቲያኑ ጠበቃ ነኝ ለምትለው ግለሰብ የቤተክርስቲያናችን አንድነትና ሰላም የሚገዳቸው አባላት ባለፈው ቅዳሜ 3/22/2014 በቤተክርስቲያናችን በመገኘት የተለያዩ ጥያቄዎችን ባቀረቡበት ወቅት ግለሰቧ ስማቸውን ለመግለጽ ያልፈለገቻቸው አንዳንድ አሁን ያሉና የቀድሞ ቦርድ አባላት በቃል በነገሩኝ መሠረት ብቻ ቤተክርስቲያኑንና ቦርዱን ወክዬ እየሰራሁ ነው ስትል የሕግ ሰው ነኝ የምትለው ግለሰብ ሕገ-ወጥነቷን በአደባባይ ገልጻለች።

በእለቱ ሕገ-ወጥ የቦርድ አባላት ሕዝቡ ተፈራርሞ ባቀረበው አጀንዳ መሠረት የአባላት ጠቅላላ ጉባዔ አንጠራም በማለት ከፍርድ ቤት በተመደቡት አደራዳሪ ዳኛ በኩል አቋማቸውን በማሳወቃቸው የቤተክርስቲያናችንን ደህንነት ለመጠበቅ እና ለማስጠበቅ እንዲሁም ሕገ-ወጥ የቦርድ ስብሰባን ለማስቆም
ወደ ቤተክርስቲያን የተመሙት ምእመናን የቤተክርስቲያኑ ጠበቃ ነኝ ስትል ከከረመችው ግለስብ ጋር ባደረጉት የጥያቄና መልስ ግብ ግብ ቤተክርስቲያናችንን ለመከፋፈልና ሰላሟን ለመንሳት እየሰሩ ያሉትን አንዳንድ የቦርድ አባላት የማጭበርበር ሥራ ያጋለጠ ነበር።

ውድ የደብረሰላም መድኃኔዓለም ምእመናን ላለፉት አንድ ዓመት ከአራት ወራት ያህል ሰላማችን ታውኮ፣ አንድነታችን ተናግቶና ሕሊናችን አዝኖና ከርሟል። ይህም ሁሉ ትዕግስት የተደረገው ለቤተክርስቲያን ሰላምና አንድነት ሲባል ነበር። ነገር ግን በአሁኑ ሰዓት በቤተክርስቲያናችን ውስጥ እንዲህ አይነት ከፍተኛ የማጭበርበር ሥራ እየተካሔደ ያለ በመሆኑና ቤተክርስቲያናችንን ፈጽሞ ለማዘጋትና ለማፍረስ እየተንቀሳቀሱ ያሉ ኃይሎች ስላሉ ቤተክርስቲያናችንን ከእንደነዚህ ዓይነት ሰርጎ ገቦች የማጽዳት ሥራ የሁላችንም መሆኑን ማወቅ ይኖርብናል። ለዚህም በመጪው ሜይ 11/2014 ዓ.ም በሚደረገው የአባላት ጠቅላላ ጉባዔ ላይ በነቂስ በመገኘት እና ኃላፊነት የሚሰማቸውን አዳዲስ የቦርድ አባላት በመምረጥ ቤተክርስቲያናችሁን እንድትታደጉ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን። ያለ ሕጋዊ ውልና ፊርማ የቤተክርስቲያናችን ጠበቃ ነኝ በማለት በውስጥ ጉዳያችን በመግባት ስትንቀሳቀስ በነበረችው ‘የሕግ
ባለሙያ’ እና ይህንንም ድርጊት ባልተሰጣቸው ስልጣን ቤተክርስቲያኑን ወክይ ብለው በቃልም ሆነ በጽሑፍ ውለታ የገቡትን ግለሰቦች በሕግ የምንጠይቅ መሆኑን እንድታውቁ እንወዳለን። የሕግ የበላይነት በሰፈነበት ሃገር እንዲህ አይነቱ ሕገ-ወጥ ድርጊት መፈጸሙ ሁላችንንም ሊያስቆጣን ይገባል።

መድኃኔዓለም የቤተክርስቲያናችንን አድነት ይጠብቅልን።

↧

Health: አስም ትናንት፣ ዛሬና ነገ –የአስም ህክምናዎችና መድሃኒቶች በቀድሞዎቹ እና በአዳዲስ ጥናቶች ውስጥ

$
0
0

ከመተንፈሻ አካል ጋር ተያይዞ የሚከሰተው የአስም ህመም ከፍተኛ ቅዝቃዜ ባለበት በዚህ በክረምት ተባብሶ የመታየት እድሉ ከፍተኛ ነው፡፡ በዚህ ቀዝቃዛማ ወቅት እኛ ላይ ይበረታሉ እንጂ ቀዝቃዛማ አየር በሚኖርበት በየትኛውም የዓለማችን ክፍል ችግሩ ተባብሶ መታየቱ አይቀርም፡፡ ይህ ችግር እንዳለ ባለበት ሁኔታ ውስጥ ታዲያ አስምን ለማከም በየጊዜው የተለያዩ ነባርም ሆኑ አዳዲስ መድሃኒቶች ህክምናውን መሰረት አድርገው በስራ ላይ ውለዋል እየዋሉም ነው፡፡ የአስም መድሃኒቶች የህመሙን መከሰትና የምልክቱ ሁኔታ በማየትና እነሱንም ለመቆጣጠር ይውላሉ፡፡ እነዚህም መድሃኒቶች በአጭር ጊዜ ውስጥ ህመሙን ሊያስታግሱ (በደቂቃ ውስጥም) ይችላሉ፡፡ በአጠቃላይ ግን የአስም መድሃኒቶች በተለያዩ ምድቦች ተከፋፍለው ይገኛሉ፡፡ እነዚህም በመድሃኒቶቹ አሰራር ላይና በሚፈጥሩት የጎንዮሽ ጉዳት ላይ የተመሰረተ ነው፡፡ አብዛኛው ሰው የሚጠቀምባቸው መድሃኒቶችም ለአጭር ጊዜ ማገገምን ለማግኘት ወይም የረዥም ጊዜ ህመሙን ለማግኘት ወይም የረዥም ጊዜ ህመሙን ለማከም በሚል የሚወሰዱ ናቸው፡፡ ሌሎቹ ደግሞ በተቀናጀ መልኩ መድሃኒቶቹን ይጠቀሙባቸዋል፡፡ የአስም ህመም በየጊዜው እንደመለዋወጡ ህመሙን ለመቆጣጠር ከቅርብ የህክምና ባለሙያ ክትትል አለመራቅ ይመረጣል፡፡ ታዲያ የአስም ህክምናዎች ከላይ ከተጠቀሰው በተጨማሪ በዕድሜ፣ በሚያሳየው ምልክትና አስቀድሞ ውጤታማ በሆነው የመድሃኒት አሰጣጥ ላይ የተመረኮዘ ይሆናል፡፡
Asthma
የረዥም ጊዜ የመድሃኒት አወሰዳደድ
የአስምን ህመም ለመቆጣጠር የረዥም ጊዜ መድሃኒት አጠቃቀማችን በየቀኑ ሊፈፀም የሚችልና ህመሙን በማስታገስ ብቻ ሳይሆን በማከም ላይ ያተኮረ ነው፡፡ ይህ ደግሞ ህመሙን ከመቆጣጠርና ከመፈወስ ጋር የተያያዘ ነው፡፡ እነዚህ ህክምናዎች ራሳቸውን የቻሉ ሆነው በተለያዩ ክፍሎች የተከፋፈሉ ናቸው፡፡ አብዛኞቹ የአስም ህክምናዎች በአየር መልክ የሚሳቡ (inhalers) እንደዚሁም ብሮንካይት አካባቢ ያሉ ጡንቻዎችን መከፋፈት ላይ (bronchodilators) ያተኮሩ ናቸው፡፡ በአጠቃላይ የመድሃኒቶቹን አከፋፈል ግን ቀጥለን እናያቸዋለን፡፡
- በትንፋሽ የሚሰጥ ኮርቲኮስቴሮይድ መድሃኒቶች (Inhaled corticosteroids) ከእነዚህም መድሃኒቶች መካከል ፍሉቲካሶን፣ ቡዲሳያናይድ፣ አዝማኮርት፣ ኤሮቢይድ የመሳሰሉትን የያዘ ነው፡፡ ይህ የመድሃኒት አይነት የመተንፈሻ አካላትን የመለብለብና የመቆጣት ስሜትን ለመቆጣጠር የሚውል ነው፡፡ ይህ በአፍ ከሚሰጠው የኮርኮስትሮይድ የተለየ ሲሆን የጎንዮሽ ጉዳቱም ዝቅተኛ ነው፡፡ ይህ መድሃኒት ታዲያ ለረዥም ቀናት ከህመም ለማገገም የሚወሰድ ነው፡፡
- ቤታ-2 አጎኒስትስ (Long-acting bets-2 agonists) ይህ ምድብ ደግሞ ሳልሜቴሮል፣ ፎርሞቴሮል የመሳሰሉትን የያዘ ነው፡፡ ይህም በትንፋሽ የሚወሰድ ሲሆን የመተንፈሻ አካላትን በመከፋፈትና የሴሎችን መቆጣት በመቀነስ ዘና በማድረግ እረፍትን የሚያሰጥ (bronchodilators) ነው፡፡
- ሌኮተሪን ሞዲፋየርስ (Leukotrine modifiers) በዚህ ምድብ ውስጥ ሞንቲሉካስት፣ ዛፊይሉካስት፣ ዛይሊውተን የመሳሰሉትን ያካተተ ሲሆን የአየር ቧንቧን በመክፈት የመከርከርና የመታፈን እንደዚሁም የንፍጥ መሰል ፈሳሽ (mucous) የበዛ ምርትን መቀነስ የሚያስችል ነው፡፡
- ክሮሞላይን እና ኔዶ ክሮማይል (cromlyon and nedocromil) ይህ ደግሞ የአስም ሕመም በተለያዩ አለርጂክ በሆኑ ነገሮች ሲቀሰቀስ የአስምን የህምም ምልክቶች ከመቀነስ ጀምሮ የአለርጂክ ችግሮቹንም ያስወግዳቸዋል፡፡
- ቲዎፓያሊይን፡- ይህ የመድሃኒት ምድብ ደግሞ የመተንፈሻ አካላትን በመከፋፈትና በዙሪያው ያሉ ጡንቻዎች ዘና እንዲሉ የሚያደርግ ነው፡፡

ፈጣን የማገገሚያ መድሃኒቶች አወሳሰድ
እነዚህ የመድሃኒቶች ምድብ በአጭር ጊዜ ውስጥ ፈጣን የማገገም ሂደትን የሚያከናውኑ ናቸው፡፡ እነዚህም የአስም ህመም ድንገት ሲመጣና አጣዳፊ ሲሆን አስቸኳይ መፍትሄን ከመስጠት አኳያ የሚውሉ ናቸው፡፡ እነዚህም፡-
- ቤታ-2 አጎኒስትስ (shoprt-acting beta-2 agonists) ከዚህ የመድሃኒት ምድብ ውስጥ አንዱ አልቡቴሮል ሲሆን ጊዜያዊና ፈጣን ምላሽን በደቂቃ ውስጥ መስጠት የሚችል ነው፡፡ የአስም ህመሙ የጠነከረ ከሆነ ግን የማገገሙ ሁኔታ ለ6 ሰዓት ብቻ ይሆንና ከዚህ ሰዓት በኋላ ተመልሶ የመምጣት ሁኔታን ሊያሳይ ይችላል፡፡
- ኢፕራትሮፒየም (Ipratropium/Atrovent) ይህ የመድሃኒት ጥቅም ደግሞ ፈጣን በሆነ መልኩ የህመሙን ምልክት የሚያጠፋና አየር በቀላሉ መውጣትና መግባት እንዲችል የሚያደርግ ነው፡፡ በተለይም የብሮንካይ ችግሮች ካሉ እንዲቀረፉ ያደርጋል፡፡
- በአፍ ወይም በደም ስር የሚሰጥ ኮርቲኮስቶሮይድስ (Oral and in travenous corticosteroids)፡- ፕሪዲናዩሲን እና ሜታይል ፕሪዲናዩሰን በዚህ ምድብ ውስጥ የሚገኙ ሲሆኑ የመተንፈሻ አካላትን ዘና በማድረግ መታፈንን በማስቀረት የአየር ቧንቧን በቅፅበት የሚከፋፍቱ ናቸው፡፡ ይህን መድሃኒት አብዝቶ መውሰዱ የጎንዮሽ ጉዳት ስለሚያመጣ የሚመከር አይደለም፡፡

አለርጂ ላይ ያተኮረ የአስም ህክምና /Allergen Immunotherapy/
ይህ የመድሃኒት ህክምና የመተንፈሻ አካላት አለርጂ ለሚሆኑባቸው ነገሮች የመቆጣት ስሜትን እንዳይፈጥሩ ወይም የሰውነት በሽታን የመከላከል ስርዓት ለአለርጂ መነሻ ለሆኑ ነገሮች ምላሽ እንዳይሰጥ በማድረግ የሚሰሩ ናቸው፡፡
- ኢሙውኖቴራፒ (Immunotherapy)
ይህ ለተወሰኑ ሳምንታት ለጥቂት ወራት የሚሰጥና በቀጣይነትም ለወራት የሚሰጥ ነው፡፡ እነዚህ መድሃኒቶች ከጊዜ በኋላ አለርጂክ ሊፈጥሩ የሚችሉ ነገሮች የሰውነታችንን የመከላከያ ኃይል በማብዛት ወደ አስም የሚሄዱበትን አጋጣሚ ይቀንሳሉ፡፡
- አንቲ-አይጂ.ኢ ሞኖክሎናል አንቲቦዲይስ (Anti-IgE Mono-clonal antibodies) ኦማሊዙማብ (ዞሌር) የሚባል መድሃኒትን የያዘ ሲሆን በመርፌ የሚሰጥ ሲሆን ከላይ ካየነው ጋር በተመሳሳይ መልኩ የሚሰጥ ነው፡፡ ልዩነቱ የሚሰጥበት የጊዜ ሁኔታ መለየት ብቻ ነው፡፡ እስከ አሁን የተቀስናቸው መድሃኒቶች አሁን ባሉበት ሁኔታ ጥቅም ይስጡ እንጂ በከፍተኛ የጥናት ምርምር ውስጥ የተሻለ ግኝትም ላይ እንዲገናኙ ለማድረግ ጥረቶች እንደቀጠሉ ናቸው፡፡

↧

ከምዕራብ ሸዋ ዞን አምቦ ዳኖ ወረዳ የተፈናቀሉ ገበሬዎች አዲስ አበባ ገቡ፤ “ብንመለስ ሊገድሉን ይችላሉ”

$
0
0

geberewoch ethiopia
ከዳዊት ሰለሞን

ተፈናቃዩቹ ከጎንደር አካባቢ ተነስተው ከዛሬ 20 ዓመት በፊት ወደ ምዕራብ ሸዋ ዞን አምቦ ዳኖ ወረዳ በመውረድ በእርሻ ስራ የተሰማሩ ገበሬዎች ናቸው፡፡ከ1996ዓ.ም ጀምሮ በተለያየ ደረጃ ‹‹ክልላችንን ለቅቃችሁ ውጡ››ሲባሉ ቆይተዋል፡፡

ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ማስፈራሪያው ወደ ግድያ፣ድብደባና ወከባ በማደጉ ለአቤቱታ አካባቢያቸውን ጥለው አዲስ አበባ ለመግባት ተገደዋል፡፡ከተፈናቃዩቹ መካከል የተወሰኑት ወደ ፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አቶ ካሳ ተ/ብርሃን ጽ/ቤት በማምራት አፈ ጉባኤውን ለማናገር ቢሞክሩም ሊያገኟቸው አልቻሉም፡፡የአፈ ጉባኤው ጸሐፊ ጉዳያችሁ ታይቷል ወደ መጣችሁበት ተመለሱ››ያለቻቸው ቢሆንም ተፈናቃዩቹ ‹‹ብንመለስ ሊገድሉን ስለሚችሉ አንመለስም››የሚል አቋም ይዘዋል፡፡

ከ26 የሚልቁ ሰዎች በአደባባይ ድብደባ ደርሶባቸው እጅና እግራቸው እንደተሰበረ የሚናገሩት ተፈናቃዩቹ‹‹አቶ ጌጡ ክብረት የተባለ ግለሰብ በገበያ ቦታ በገጀራ ተቆራርጦ ህይወቱ ማለፉን በሀዘን ስሜት ተውጠው ይናገራሉ፡፡ በአዲስ አበባ ማረፊያ ባለማግኘታቸው ለችግር መጋለጣቸውን የሚገልጹት ተፈናቃዩቹ ወደ አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ጽ/ቤት በመምጣት ‹‹ፍትህ እንድናገኝ ለኢትዩጵያ ህዝብ ሰቆቃችንን አሰሙልን››በማለት ተማጽነዋል፡፡

የአንድነት ፓርቲ ዋና ጸሐፊ አቶ ስዩም መንገሻ ‹‹ህገ መንግስቱ በግልጽ እያንዳንዱ ዜጋ በፈለገው ክልል በመሄድ ንብረት ማፍራት እንደሚችል ቢደነግግም መሬት ላይ ያለው እውነታ ግን ህገ ወጥና አስቸጋሪ ነው››ብለዋል፡፡

↧

Sport: የዩክሬይን ፖለቲካና እግርኳስ

$
0
0

ራሺያ የ2018ቱ የዓለም ዋንጫ አዘጋጅ ሀገር ናት፡፡ የፊፋ አባል የሆነችውን የዩክሬይንን ሉዓላዊ ግዛት በኋይል የያዘችው ሀገር ዓለምአቀፉ የእግርኳስ ውድድርን ልታዘጋጅ እንደማይገባት በመናገር ፕሬዝዳንቷ ቭላዲሚር ፑቲን አቋማቸውን መለስ ብለው እንዲመረምሩ ለማድረግ የሚሞክሩ ወገኖች አሉ፡፡ የእግርኳስ ባለስልጣናት ግን ይህን መሰሉን ንትርክ መስማትን አይፈልጉም፡፡ ‹‹ስፖርትና ፖለቲካ ተለያይተው መታየት ይገባቸዋል›› በሚለው አቋማቸው መፅናትን ይመርጣሉ፡፡ የቤላሩስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትርም እንደ ፊፋ እና የአውሮፓ እግርኳስ ማህበር ባለስልጣናት ሁሉ ስፖርትና ፖለቲካ በተለያዩ አይነቶች መታየት እንደሚገባቸው ተናግረዋል፡፡ እውን እግርኳስና ፖለቲካ ሊነጣጠሉ ይችላሉ?
putin
በአንዳንድ እግርኳስ ክለቦች ውስጥ እግርኳስና ፖለቲካ ተነጣጥለው ይታያሉ፡፡ የጀርመኑ ሼልክ 04 አንዱ ተጠቃሽ ነው፡፡ በሩህር ከተማ በሚገኙ ኩሩ ላብ አደሮች የሚደገፈው ክለብ በእነዚህ ደጋፊዎቹ ባለቤትነት በፍፁም ዴሞክራሲያዊ መርሆዎችና በማህበረሰብ ደንቦች ይመራል፡፡ ደጋፊዎች በክለቡ ዕጣ ፈንታ ላይ የመወሰን ድምፅ አላቸው፡፡ በተወሰነ ደረጃም በፖሊሲዎች ላይ ለውጥ የማድረግ ስልጣን አላቸው፡፡ ለምሳሌ፡- ባለፈው ዓመት የኢንተርኔት የቲኬት ሻጭ ከሆነው ኩባንያ (ቪያሳጎ) ጋር ክለቡ የፈጠረውን አወዛጋቢ ትብብር መልሶ እንዲያጤነው አስገድደውታል፡፡ የሼልክ ፕሬዝዳንት ከሌመንስ ቶኒስ ከራሺያው ፕሬዝዳንት ፑቲን ጋር እጅግ የጠበቀ ግንኙነት እንዳላቸው ይታወቃል፡፡ የማሊያ ላይ ስፖንሰር Gazprom ፑቲን የሚመሩት የራሺያ መንግስት በባለቤትነት የያዘው የኢነርጂ ኩባንያ ሲሆን ለጀርመኑ ክለብ በዓመት 16 ሚሊዮን ዩሮ ይከፍላል፡፡
Gazprom የራሺያው ክለብ ዜኒት ሴንት ፒተርስበርግ አብላጫ ባለድርሻ መሆኑም ይታወቃል፡፡ ፕሬዝዳንት ፑቲንና ጠቅላይ ሚኒስትር ዲሚትሪ ሜድቨዴቭ ደግሞ የዜኒት ደጋፊ ብቻ ሳይሆኑ በኮሚዩኒስቶቹ ዘመን ሌኒንግራድ ተብላ ትጠራ የነበረው የሴንት ፒተርስበርግ ከተማ ተወላጆች ናቸው፡፡ ፑቲን በሀገራቸው ክለብ ላይ ያላቸው ቀጥተኛ ተፅዕኖ ሰሞኑን ከዩክሬይን ጋር በፈጠሩት የፖለቲካ ትኩሳት ፈተና አይገጥመውም፡፡ ሆኖም የሼልክን የመሰለው ድንበር ዘለል እግርኳሳዊ ግንኙነታቸው ላይ ፖለቲካዊ እርምጃዎች ጥላ አያጠላም ማለት አይቻልም፡፡
ፑቲን የክሬሚያን ባህር ገብ ግዛት በወታደሮቻቸው ቁጥጥር ስር በማድረጋቸው ከዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ጫናዎች እየደረሰባቸው መሆኑ ይታወቃል፡፡ አንዳንድ የሼልክ ደጋፊዎችም ባላቸው የመወሰን መብት በመጠቀም ክለባቸው ከፑቲን ጋር ያለውን ግንኙነት እንዲያቋርጥ እየጠየቁ ይገኛሉ፡፡
ደጋፊዎቹ በሚያሳትሙት ‹‹Schalke unser›› በተሰኘው መፅሔትም የክለቡን ቦርድ ራሱን ከፑቲን እንዲያርቅ የሚጠይቁ ይፋዊ ደብዳቤ መላኩ ታውቋል፡፡

‹‹ሼልክ እግርኳስ ክለብ ዴሞክራሲያዊ መሰረት ያለው ክለብ ነው፡፡ ሀሳብን የመግለፅ ነፃነትንም በከፍተኛ ደረጃ ያከብራል›› ይላል በመፅሔቱ ላይ አስተያየቱን ያሰፈረው ሮማን ኮልበ፡፡ ‹‹እናም (እንደ ፑቲን ያለውን) አምባገነን ማገልገል የለብንም›› ሲል ያክላል፡፡ በደብዳቤውም ላይ ይኸው መልእክት በግልፅ ሰፍሯል፡፡ ደብዳቤው በክሬሚያ ባህር ገብ ምድር በተፈጠረው የፖለቲካ ቀውስ ብቻ ሳይሆን ፕሬዝዳንት ፑቲን ፖለቲካ እና ስፖርት መለያየት እንደሚገባቸው በተግባር ለማሳየት ሲሉ ከሼልክ ቡድን አባላት ለመገናኘት ግብዣ ለማቅረባቸው የተሰጠ መልስም ነው፡፡ ግብዣውን ከላኩበት ሰዓት ብዙም ሳይቆይ ወታደሮቻቸውን ወደ ክሬሚያ እንዲገቡ አዝዘዋል፡፡

ፑቲን ከክሬሚያ ጋር በተያያዘ የተለያዩ ተፅዕኖዎች እየተደረጉባቸው ባለበት በዚህ ሰዓትም ቢሆን ግብዣውን አልሰረዙም፡፡ ደጋፊዎች ክለባቸው ግብዣውን እንዳይቀበል በጠየቁበት ባለፈው ሳምንት የሼልክ ጄኔራል ማናጀር ሆርስት ሄሉድት ቡድኑ ወደ ሞስኮው የመሄድ ምንም አይነት እቅድ እንደሌለው ባዘጋጁት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ አስታውቀዋል፡፡

የጉዞ ዕቅድ አለመያዙ ብዙዎችን የሼልክ ደጋፊዎች እፎይ የሚያሰኝ ነው፡፡ ዓለም ፑቲን ላይ ጫናውን በጨመረበት ወቅት ላይ ዩሊያ ድራክስሰር፣ ክላስ ያንሁንቴላር እና ኬቨን ፕሪንስ ቦአቴንግን የመሳሰሉት ተጨዋቾች ፕሬዝዳንቱን ለመጎብኘት ቢሄዱ እጅግ አሳፋሪ ይሆን ነበር፡፡ ኦፊሴላዊው ጉብኝት ባይኖር እንኳን የሼልክ እና የፑቲን ግንኙነት ጠንካራ መሆኑን አሁንም እንደቀጠለ ነው፡፡ የሼልክ ሊቀመንበር ክሌመንስ ቶኒስ ከፕሬዝዳንቱ ጋር የቀረበ የግል ወዳጅነትም አላቸው፡፡
ባለፈው ጃንዋሪ ቶኒስ ክለቡን በራሳቸው ዕቅድ ከዕዳ ነፃ እንደሚያደርጉት ቃል ገብተው ነበር፡፡ በስጋ ንግድ የታወቁት እኚሁ ቱጃር ባለፉት ሁለት ዓመታት ብቻ የሼልክን ዕዳ በ50 ሚሊዮን ዩሮ እንዲቀንስ አድርገዋል፡፡ ክለቡ አሁንም 170 ሚሊዮን ዩሮ ዕዳ ተሸክሟል፡፡ ስለዚህ ሼልክ ከዕዳ ነፃ የመሆን እቅዱን ተግባራዊ ለማድረግ Gazprom ያስፈልገዋል፡፡ የስፖንሰሮቹ ስምምነትም በቅርቡ እስከ 2017 ድረስ ተራዝሟል፡፡ ሼልክ እንዳለፈባቸው ፈተናዎችና እንደ ቀድሞ አሰልጣኙ ፌሊክስ ማጋት የተጨዋቾች ግዢ ፖሊሲ ዕዳው ከዚህ በላይ በናረ ነበር፡፡ Gazprom ከጎኑ መኖሩ ከተባባሰ የፋይናንስ ቀውስ እንዲድን አስችሎታል፡፡ ይህም ሊቀመንበር ቶኒስ ከፕሬዝዳንት ፑቲን ጋር ባላቸው ቅርበት የተወሰነ ጉዳይ መሆኑ አያጠራጥርም፡፡

ሊቀመንበሩም ሆኑ የክለቡ ባለስልጣናት የራሺያው ኩባንያ ጋር ባላቸው ግንኙነት መጠቀማቸውን ስለሚያውቁ ራሳቸውን ከፒቱን ለማራቅ አልወሰኑም፡፡ እንዲያውም ክለቡ ለሱዶቼ ዜይቱንግ ጋዜጣ በሰጠው መግለጫ ከ Gazprom ጋር ያላቸው ግንኙነት ‹‹የታመነና ገንቢ›› መሆኑን አስታውቋል፡፡ ቶኒስ ስለ ፑቲን ጉዳይ ሳይናገሩ አልቀሩም፡፡ ክለባቸውም ግንኙነቱን ከኩባንያው ጋር ብቻ እንዲሆን በመገደብ እየተንቀሳቀሰ መሆኑን ማስታወቁን በመምረጥ ማንም ሰው ጥርጣሬ ውስጥ እንዳይገባ ለማድረግ ሞክረዋል፡፡ ከዚህ ቀደም ቶኒስ ባደረጓቸው የተለያዩ ቃለ ምልልሶች ላይ ከፕሬዝዳንት ፑቲን ጋር በተገናኙ ቁጥር ሁለት ነገሮችን በስጦታ መልክ እንደሚያበረክቱላቸው ተናግረዋል፡፡ የሚያመርቱትን ስጋ ናሙና እና ሼልከን ማሊያ መሆኑ ነው፡፡ በ2012 በኮሎኝ ከተማ ከሚታተመው ‹‹ኤክስፕረስ›› ጋዜጣ ጋር ባደረጉት ቆይታ ቶኒስ ፑቲንን ‹‹ደስታን አብረው ሊካፈሏቸው የሚመቹ ሰው›› ሲሉ ገልፀዋቸው ነበር፡፡ አክለውም ‹‹በጣም ጥሩ ምግብ አብሳይ እና አንዳንድ ጊዜም ማሳቅን የሚወዱ›› መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡ በፖለቲካዊ ጉዳዮች ላይ ፑቲን ስላላቸው አመርቂ ያልሆነ ሪከርድ ሲጠየቁም የሼልከው ሊቀመንበር ንፅፅራዊ መልስ መስጠትን መርጠዋል፡፡ ‹‹የራሺያንና የጀርመንን ዴሞክራሲዎችን ማወዳደር አይቻልም›› ካሉ በኋላ በፑቲን አመራር ስር በራሺያ ብዙ ነገሮች በአዎንታዊ ዕድገት ማሳየታቸውን ጠቅሰዋል፡፡

የሰሞኑ የክሬሚያ ቀውስ እስኪነሳ ድረስ ፑቲንን ማሞገስ በሼልክ መጥፎ አልነበረም፡፡ አሁን ግን ነገሮች ተቀይረዋል፡፡ ደጋፊዎች ተቆጥተዋል፡፡ የደጋፊዎቹን መፅሔት የሚያዘጋጀው ሮማን ኮልበ እንደሚናገረው የሼልክ ወዳጆች ቡድን ከፑቲን ጋር እንዲገናኙ ፈፅሞ አይፈልጉም፡፡ ‹‹በቅርቡም ፒቱንና ጋዝፕሮምን የሚቃወሙ የጨረቃ ላይ ፅሑፎች በስታዲየሙ ውስጥ ብንመለከት አልገረምም›› ብሏል፡፡

በዚህ መልኩ ተቃውሞን ማሰማት ምን ያህል ውጤታማ እንደሆነ ለማየት ጊዜ ያስፈልገናል፡፡ ሆኖም ስፖርትና ፖለቲካ እርስ በርሳቸው ለመተሳሰራቸው የሼልክ እና የፑቲን ጉዳይ ጥሩ ማስረጃ ነው፡፡ ሼል ከራሺያ ጋር ባለው ስራ ግንኙነት እጅጉን መጠቀሙ የሚክድ የለም፡፡ ይህም በተወሰነ መልኩም ከራሺያ ጋር አቆራኝቶታል፡፡ Gazprom የዓለማችን ግዙፍ የተፈጥሮ ጋዝ አምራችና አቅራቢ ሲሆን ከፕላኔታችን ታላላቅ ኩባንያዎች አንዱ ነው፡፡ ቃሉ ‹‹የጋዝ ኢንዱስትሪ›› የሚል ትርጉም ይሰጣል፡፡ በ2011 ብቻ 513.2 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሜትርስ የተፈጥሮ ጋዝ አምርቷል፡፡ በዚያው ዓመት ራሺያ ከዓመታዊ ገቢ 8 በመቶ ያህሉን ያገኘችው ከጋዝፕሮም ንግድ ነው፡፡ በ2012 ደግሞ 153 ሚሊዮን ዶላር ገቢ አስመዝግቧል፡፡ 35 ሺ ሰራተኞች ካሉት ከዚህ ተቋም ጋር ክለባቸው ያለው ግንኙነት እንዳይቋረጥ የሚፈልጉ ደጋፊዎች ቁጥር ጥቂት እንደማይሆን እርግጥ ነው፡፡ ሆኖም ከፑቲንና ከጋዝፕሮም ጋር የክለባቸው ስም አብሮ በመጠራቱ ቅር የሚሰኙ መብዛታቸው አያጠራጥርም፡፡ የሼልክን እግርኳሳዊ ውርስ እሴቶቹን ያቆሽሻል የሚል እምነት ያሳድርባቸዋል፡፡ ከጊልሴንኪርችን ከተማ ውጭም ይዘላል፡፡

በሀገሪቱ ትልቁ የክለቦች ውድድር ዋና ዋና ስፖንሰሮች አንዱ ለመሆን ከአውሮፓ እግር ኳስ ማህበር ጋር በመስማማቱ ጋዝፕሮም በጨዋታዎች ላይ በሜዳው ዙሪያ ባለው የማስታወቂያ ሰሌዳ ላይ በጉልህ ይታያል፡፡ በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግም ከቼልሲ እግርኳስ ክለብ አበይት ፓርትነሮች አንዱ ነው፡፡ የክሬሚያን ቀውስ ከራሺያ መንግስት እና ቭላዲሚር ፑቲን እንዲሁ አይነጣጠሉም፡፡ የራሺያ መንግስት ኩባንያ የሆነውና ፑቲን በቀጥታ የሚያዙበት ከጋዝፕሮም ጋር ግንኙነቱን የጠበቀ በተለይ የምዕራብ አውሮፓ ሀገር ክለብ ደግሞ ከሞራል ጥያቄዎች የማይሸሽበት ጊዜ ላይ እንገኛለን፡፡ ፖለቲካና ስፖርትም የማይነጣጠሉበት ዘመን ላይ ደርሰናል፡፡

↧
↧

[የሃረሩ እሳት ቃጠሎ ጉዳይ] –የእሳት ፖለቲካ በኢትዮጵያ (Fire Politics in Ethiopia) –ይሄይስ አእምሮ

$
0
0

harar city fire
በሃይማኖት መሪዎችና አገልጋዮች ዙሪያ ሰሞኑን አንዲት መጣጥፍ ጽፌ ለድረ ገፆች ልኬ ነበር፡፡ ለኅሊናቸው ተገዢ የሆኑ አወጡት – አስነበቡን፤ እግዚአብሔር ይስጣቸው፡፡ ለባህልና ለይሉኝታ ያደሩት እንዲሁም እነሱ በሚፈልጉት ሙዚቃ ብቻ ታንጎና ማሪንጌ መደነስ የሚፈልጉት ወደቅርጫታቸው ከተቱት – ይክተቱት፡፡ ሁሉም የመሰለውን የማድረግ መብት አለውና ያነበበም ያስነበበም፣ ያፈነም ያሳፈነም የኅሊናው ዳኝነት ይፍረደው ከማለት ውጪ በዚህ በውዥንብር ዘመን መወቃቀሱም ሆነ መካሰሱ ፋይዳ የለውም፡፡ ግን ግን የእውነት አምላክ ለሁላችንም እውነተኛውን የልቦናና የኅሊና ሚዛን እንዲሰጠን እጸልያለሁ፡፡ ሁለትና ሁለት ሲደመር አራት ብቻ የሚሆንበት ሃቀኛ ዘመን እንዲመጣልንም እንዲሁ፡፡ በተረፈ የልጆቼ ልጆች “Mother stomach is ranger.” ሲሉ እሰማለሁና በዚያ “ሜጀር” የተቃኘ የቅሬታ ዘፈኔን ጋብዣቸው በገዢዎቻችን አነጋገር ንቅድሚት እላለሁ፤ ሕይወት እንዲህ ናትና፡፡

አንድ የብዕር ወዳጄ ያቺን መጣጥፍ ካነበበ በኋላ በነካ እጄ በዚህች ወያኔያዊ የእሳት ፖለቲካ ላይ ጥቂት ነገር እንድል አሳሰበኝ፡፡ ርዕሲቱንም የሰጠኝ እርሱ ራሱ ነው – Please take the credit dear Mr. Thingummy, wherever you may be.

ሀገራችን ተመልካች ያጣ የሕዝብ ብዛት ብቻ ሣይሆን ጭንቅት የሚያዞሩ እጅግ በርካታ ችግሮች የሚርመሰመሱባት በመሆኗ አንባቢን ላለማስቸገር ወይም ብዙ አንባቢ የለም በሚል ተስፋ መቁረጥ ወይም “አድማጭና የእርምት እርምጃ ወሳጅ ኃላፊነት የሚሰማው ጤናማ ወገን በሌለበት የኳስ አበደች ሀገራዊ ምስቅልቅል ሁኔታ ውስጥ ተነቦስ ምን ፋይዳ ሊያመጣ?” ከሚል ብሶት የተነሣ ሆን ብለን እየተውነው እንጂ መጻፍ የምንፈልግ ዜጎች የምንጽፈበት ጉዳይ በሽበሽ ነው፤ በበኩሌ አድማጭ ቢኖር ሃያ አራት ሰዓት ብጽፍ የማይደክመኝና የሚያጽፍ ጉዳይም ሞልቶ የተረፈ መሆኑን የምገልጸው የሚያፍኑኝን ድረ ገፆች ደስ አይበላቸው በሚል የመከፋት ስሜት ሳይሆን ተናግረን አድማጭ ባለመኖሩ ሳቢያ በእጅጉ የምቆረቆር መሆኔን በሚጠቁም የቁጭት ስሜት ነው፡፡ የወያኔው የዘረኝነት አባዜ ካስከተለብን ተነግሮ የማያልቅ ሰቆቃና የግፍ አስተዳደር ጀምሮ እነሚሚ ስብሃቱን የመሳሰሉ የሥርዓቱ ዘውጋዊ አባላትና እበላ ባይ ሆዳም ደጋፊዎቻቸው ባቋቋሟቸው የሠራተኛ አስቀጣሪ ድርጅቶች አማካይነት የሚካሄደውን ዘመናዊ ባርነት ብንመለከት ጉዳችን በጽሑፍም ሆነ በቃል ተዘርዝሮ የማያልቅ አስገራሚ ፍጡራን ሆነናል – እኛ “ኢትዮጵያውያን”፡፡ ቴዲ አፍሮ “እዚህ ጋ’ም እሳት፣ እዚያ ጋ’ም እሳት፣ እሳት፣ እሳት፣እሳት…” ሲል እንዳቀነቀነው ሀገራችን ወያኔያዊ እቶን ላይ ተጥዳ በየአቅጣጫው እንደባቄላ አሹቅ እየተንገረገበች ናት፡፡ ፖለቲካው እሳት፣ ሃይማኖቱ እሳት፣ ፌዴራሉ እሳት፣ ፖሊሱ እሳት፣ ቀኑና ሣምንቱ እሳት፣ ወሩና ዓመቱ እሳት፣ ኑሮው እሳት፣ ባለሥልጣናቱ እሳት፣ ነጋዴው እሳት፣ ዳኛው እሳት፣ በሽታው እሳት፣ ርሀቡ እሳት፣…፡፡ ሁሉም በእሳት አለንጋ ይጋረፋል፤ ይጠብሳል፤ ይሸነቁጣል፤ የት እንድረስ? የትስ እንግባ? ከነዚህ ከሲዖል ካመለጡ ሽፍቶች የሚታደገን ማን ነው? አምላከ ኢትዮጵያ ወዴት አለ? ኤሎሄ! ኤሎሄ! ኤሎሁም! በዚህ መከራችን ላይ ነው እንግዲህ ወያኔ በሐረርም በአዲስ አበባም እንደዚያች ተዘውትራ እንደሚነገርላትና “እዚህ አካባቢ እሳት ይነሳል ብያለሁ” ብላ ባስጠነቀቀች ማግስት ራሷ እንደምትለኩሰው የደሴዋ ዕብድ ሴት በሹምባሾቹ አማካይነት በሚፈልጋቸው ቦታዎች ላይ እሳት እየለኮሰ፣ እንዳይጠፋም ከልካይ ዘብ እያቆመ በሀገር ሀብትና በሕዝብ ዕንባ እየተዝናና የሚገኘው፡፡ ለማንኛውም አስታዋሼን ላመስግንና በጠቆመኝ ሃሳብ ዙሪያ እንዳመጣብኝ ትንሽ ልብከንከን፡፡ እውነትን ላለማየት ዐይነ ኅሊናቸው የታወረ፣ እውነትን ላለመስማት ዕዝነ ልቦናቸው የተደፈነ፣ አእምሯቸው በፀረ-ለውጥ ቫይረስ ለፈውስ ባስቸገረ ሁኔታ “corrupted” ለሆነ የ“ሚዲያ ሰዎች”ም የቮልቴርን አባባል ባስታውሳቸው ቅር አይለኝም – ቮልቴር እንዲህ አለ አሉ፡- “በምትናገረው ሁሉ ባልስማማም መናገር የምትፈልገውን ጉዳይ በነፃነት መናገር እንድትችል ግን ሕይወቴንም ቢሆን እገብርልሃለሁ!” አይ ኢትዮጵያ! በሁሉም ድሃ፡፡ ግን ተስፋ አለኝ – ትልቅ ተስፋ፡- ወደፊት አንድ ቀን ይህ ሁሉ ድንቁርናችንና ከንቱ ትምክህታችን እንደጤዛ ሲረግፍልን ሰው እንደምንሆን፡፡
harar
በዓለማችን የፖለቲካ ዓይነቶች ብዙ መሆናቸው ከናንተ የተሠወረ አይደለም፡፡ የድንበር ፖለቲካ፣ የውኃ ፖለቲካ፣ የዘር ፖለቲካ፣ የዘውግ ፖለቲካ፣ የውጭ ብድርና ዕርዳታ ፖለቲካ፣ የሀገር ውስጥ የድርቅ ጊዜና የርሀብ ወቅት ዕርዳታ ፖለቲካ፣ የሃይማኖት ፖለቲካ፣ … ዝርዝሩ ብዙና ኪስን ሳይሆን አንጎልን የሚቀድ ነው፡፡ ወያኔ በኢትዮጵያ ላይ ያልሞከረው የፖለቲካ ዓይነት ደግሞ የለም፡፡ እርግጥ ነው ወያኔ ብቻውን አይደለም፡፡ ይህ ቀረሽ የማይባል ሁለንተናዊ ድጋፍ ለወያኔዎች በገፍ እየሰጡ በ17 ዓመታት ውስጥ የሰው ኃይሉን ከሰባት ሰውነት ወደሚሊዮንነት በማሳደግ ፀረ-ኢትዮጵያ አቋማቸውን በተግባር የገለጡት የውጭ ጠላቶቻችንም በዚህ ኢትዮጵያን ወደፖለቲካዊ ቤተ ሙከራነት የመለወጡ ሂደት ውስጥ ያሳዩት ጉልህ ተሳትፎም ለአፍታ የሚዘነጋ አይደለም፡፡ ከዓለም ሕዝቦች መካከል እኛ ኢትዮጵያውያን ላይ ያልተፈተሸ ፖለቲካዊ መርዝ የለም፡፡ ባጭሩ የወያኔ ብቻ ሣይሆን የፈረንጆቹም guinea pig ሆነን የቀረን ብቸኛ መዘባበቻ ዜጎች ብንኖር እኛ ኢትዮጵያውያን ነን፡፡ እርግጥ ነው እነኢራቅንና አፍጋኒስታንን ብንረሳ አግባብ አይደለም – እኛን እየገረፈን ያለው የኃያላኑ የእሳት ወላፈን እነሱንም እየጠበሰ ነውና፡፡ “አልማሊኪ ቡሽ፣ ካርዛይ ቡሽና መለስ ቡሽ እያሉ ሃቀኛ ሰላም አይኖርም፡፡”

ወያኔ ተግባር ላይ ካዋላቸው ሕዝብን የማሰቃያና ሀገርን የማውደሚያ መንገዶች አንደኛው እሳት ነው፡፡ እንዲህ የምላችሁ ወዳጄ አሁን ስላስታወሰኝ ብቻ እንዳይመስላችሁ፡፡ ከጥንትም በሚገባ አውቀዋለሁ፡፡ ለነገሩ ጨካኝና አምባገነን መንግሥታት ለዓላማቸው ስኬት የማያደርጉት ነገር የለም፡፡ ደርግም በተወሰነ ደረጃ ይህን የእሳት ፖለቲካ ይጠቀምበት እንደነበር በጊዜው ሰምቻለሁ፡፡ ሞኙ ደርግ እሳትን ይጠቀምበት የነበረው ኮንትሮባንድን ከመቆጣጠር አንጻርና በጣም በጥንቃቄ እንደነበር በወቅቱ የነበሩ አሁን ድረስ ያስታውሳሉ፡፡ የወያኔ ግን የተለዬ ነው፡፡
በመሠረቱ ወያኔ ምን እንደሆነ መናገር የዐዋጁን በጆሮ ነው፡፡ ይሁንና ወያኔዎች በተጣባቸው የትውልድ መርገምት ምክንያትም ይሁን በሌላ ከሆዳቸውና ያሻቸውን እንዲሠሩ ከሚጠቅማቸው የጨበጡት ሥልጣን በስተቀር የኢትዮጵያዊነት ስሜት በጭራሽ የሌላቸው፣ እንዲያውም ከያዙት ጥቅምና ሥልጣን ያስወግደናል ብለው የሚፈሩት በቀን ሰመመንና በሌት ቅዠት የሚያባትታቸው የኢትዮጵያዊነት ስሜት በመሆኑ ኢትዮጵያዊ ነኝ የሚልን ዜጋ ሁሉ በየሄደበት እያሳደዱና እየገደሉ በደም ባሕር እየዋኙ የሚኖሩ፣ ጥላቸውንም የማያምኑ የከተማ ወሮበሎች መሆናቸውን እዚህም ላይ በድጋሚ ማስታወሱ በአሰልችነት ሊያስወቅስ አይገባም፡፡ እናም አስታውሱ – ወያኔ የዜጎችን የላብ ውጤት የሆነ ሀብትና ንብረታቸውን ማቃጠል ብቻም ሣይሆን ሕዝብን በሠልፍ ኮልኩሎ እንደሂትለር የኦሽትዊዝ ቻምበር የማይፈልጋቸውን በጋዝ እየለበለበ ቢፈጃቸው የሰይጣናዊ ተፈጥሮው የሞራል ምሰሶ ክፋትና ጥፋት ነውና ደስታን የሚያስገኝለት እንጂ ሰብኣዊነት የሚሰማው ሩህሩህ ፍጡር አይደለም፡፡ ሰብኣዊነትና ወያኔ ዐይንና ናጫ ናቸው፡፡

ወያኔዎች እንደገቡ ሰሞን የምንሰማቸው ብዙ የእሳት አደጋዎች ነበሩ፡፡ እነዚያ እሳቶች እንደሰሞነኞቹ የሕዝብን አንጡራ ሀብትና ገንዘብ ለማቃጠል የታለሙ ሣይሆኑ ጫካና ደን የማያውቁት መደዴዎቹ ወያኔዎች ደቡብ ኢትዮጵያንም እንደሰሜኑ የሀገራችን ክፍል ለማራቆት የታቀዱ ደኖችን የማቃጠል ወያኔያዊ የክተት ዘመቻዎች ነበሩ፡፡ በርካታ የደቡብና የኦሮሞ ብሔር መኖሪያ አካባቢዎች በነዚያ ወያኔ በቀሰቀሳቸው የሰደድ እሳቶች ተቃጥለዋል – አንጀታቸው ለተፈጥሮም የሚጨክን አረመኔዎች ናቸው፡፡ በምክንያትነት ሲቀርብ የነበረው ግን የኦነግን ሸማቂዎች ከምንጫቸው ለማድረቅና መደበቂያ ቦታ ለማሳጣት የሚል ነበር፡፡ ትግራይ ውስጥ ወያኔን ሊደብቅ የሚችል ዋሻ ካልሆነ በስተቀር ደንና ጫካ እንዳልነበረ ይታወቃል፡፡ ሆኖም ግን ጫካ ቢኖር ኖሮ ወያኔን ለማጥፋት በሚል ሰበብ የደርግ መንግሥት ነዳጅ በቦቴ መኪናዎች ጫካ ውስጥ እየደፋ በአብሪ ጥይትም በአሻጋሪ እየለኮሰ ሀገር ለማቃጠል የሚያበቃው የሞራል ድቀት ውስጥ እንዳልነበረ ያንጀቴን እመሰክራለሁ – ሰው ካልሞተ ሚስትም ካልተፈታች ወይ ካልሞተች አይመሰገኑም ወንድማለም፡፡ ደርግ ዜጎችንና ሀገርን በእሳት አይቀጣም፤ ደርግ ኢትዮጵያዊ ጨካኝ እንጂ እንደወያኔ ወፍዘራሽ የባንዳ ውላጅ አልነበረም፡፡ እሳት ባለጌ ነው፡፡ እሳት እጅግ መጥፎ ነው፡፡ ምሕረትን አያውቅም፡፡ እንኳንስ ዜጋህን ጠላትህንም ቢሆን በአግባቡ ውጋው እንጂ፣ በአግባቡ ቅጣው እንጂ ኢ-ሰብኣዊ በሆነ ሁኔታ በእሳት አትገርፈውም፡፡ እነሂትለርና ሙሶሊኒ እንኳንስ ዜጎቻቸውን ጠላቶቻቸውንም ቢሆን በሰደድ እሳት አልቀጡም፤ በእሳት መቅጣት የጀግና ሙያ ሳይሆን የፈሪ ዱላ ነው፡፡ ወያኔ ግን ከየትኛው የጀሃነብ ሰማይ እንደወረደብን አይታወቅም ይሄውና ጫካና ደንን ከማቃጠል አልፎ የምሥኪን ዜጎችን ቤትና ንብረት እንዳሻው በሚያዛቸው ኅሊናቢስ ጀሌዎቹ እያቃጠለ ይገኛል፡፡ ወያኔ እኮ በእሳትም ብቻ ሳይሆን እንደተራ ተንኮለኛ ዜጋ ምግብንና መጠጥን በመመረዝና የታወቀ ጠንቋይ ቤት ድረስም በመሄድ የሚጠላቸውን የሚያስወግድ ጉደኛ ፍጡር ነው፡፡ ኪሮስ አለማየሁ እንዴት ሞተ? አለማየሁ አቶምሳስ? በውነት ቆሻሾች ናቸው፡፡ ምን አድርገን ይሆን ፈጣሪ እነዚህ ለቅጣት የሰጠን ግን? እስኪ ወደዬኅሊና ጓዳችን እንግባና ራሳችንን በቅጡ እንመርምር፡፡

በዚያን ሰሞን ሐረር ውስጥ የተቃጠለው መንደር የዚሁ የወያኔን ዜጎችን በእሳት የመቅጣት የእሳት ፖለቲካ ያሳያል፡፡ የኢትዮጵያን ገንዘብ ለራሱ ፖለቲካ በመጠቀም ዜጎችን በአነስተኛና ቀጫጭን የሚባል አዲስ ፈሊጥ እያደራጀ አንዱን ርሃብተኛ ሌላውን ጥጋበኛ እያደረገ እናያለን፡፡ በጥቃቅን የማይደራጅን በጠላትነት በመፈረጅ በገቡበት እየገባ ያሳድዳቸዋል፡፡ ከወያኔ የተለዬ ነጋዴ ኑሮውና ግብሩ እሳት ሆነው እንዲያቃጥሉትና ከሀገር እንዲጠፋ ወይም በርሀብ አለንጋ ተገርፎ እንዲሞት ሲደረግ ወያኔን የተጠጋ ሆድ አደር ግን እምብርቱ እስኪገለበጥ እየበላና እየጠጣ ተንደላቅቆ ይኖራል፡፡ እንዲህ እንዲኖርም በመዥገሮች የተወረረችው እናት ሀገር በወያኔዎቹ አማካይነት ለአንዱ የእንጀራ እናት ለሌላው ደግሞ የእውነት እናት ሆና ለሆዳም ጥገኞቹ ሁሉንም ነገር እያመቻቸችላቸው ትገኛለች፡፡ ለምሳሌ በወያኔ ማኅበር ያልተደራጀ ዜጋ ሁለት በሁለት ለሆነች የንግድ ቤት ከገቢው ጋር ፈጽሞ የማይመጣጠን እጅግ ከፍተኛ ኪራይና ግብር እንዲከፍል ሲገደድ (ሂድ አትበለው እንዲሄድ ግን አድርገው በሚሉት ፈሊጣቸው) ለሆዳሞቹ ግን ካስፈለገ ካለኪራይና ካለአንዳች ግብር በሕዝብ ገንዘብ እንደፈለጉ ይሆናሉ፡፡ ባንኮች ሳይቀሩ ለነሱ የግል ጥገቶች ናቸው፡፡ የሀገር ስሜት ዛሬ ያልጠፋ ታዲያ መቼ ይጥፋ?
ይህ መሰሉና ሌላው ግፍ ሁሉ አልበቃ ብሎ ነው እንግዲህ የእሳቱ ፖለቲካ በሀገር ደረጃ እየተፋፋመ የሚገኘው፡፡ እንደሰማነው በሐረር ከአንዴም ሁለት ጊዜ ቃጠሎ ተነስቶ በብዙ ሚሊዮን የሚገመት ብርና ሀብትና ንብረት ወድሟል፡፡ ይህ የሆነው በወያኔው ፈቃድና ይሁንታ መሆኑን የምንረዳበት መንገድ ደግሞ እሳቱን ለማጥፋት ጥረት ሲደረግ አስቀድሞ የተዘጋጀው የወያኔ ጦር እሳቱን ከብቦ አላሰቀርብም ማለቱና የእሳት አደጋ ሠራተኞችም እሳቱ የሚፈለገውን ጥፋት ካገባደደ በኋላ ሥራቸውን እንዲሠሩ መፈቀዱ ነው፡፡ ይህ ዓይነቱ ግፍ ከኢትዮጵያ ውጪ የሚደረግ አይመስለኝም፤ እንዲያውም አይደረግም፡፡ ምክንያቱም የሀገር ዜግነቱን የካደና ሀገር እየቸረቸረ የሚሸጥ የሀገር መሪ ከኢትዮጵያ ውጪ በየትም ሥፍራ ይኖራል ብዬ አላምንምና፡፡

የሐረሩ እሳት መንስኤው ወያኔ ሆኖ ዓላማው ደግሞ ቦታውን ለወያኔያዊ ባለሀብቶች ለመስጠትና በእግረ መንገድም ተቀናቃኝ ኢ-ወያኔያዊ ባለሀብቶችን ለማክሰም ነው – ይህን እውነት ለማወቅ ጠንቋይ መቀለብ አያስፈልግም፡፡ በጣም ግልጽ ነው፡፡ መንታ ዓላማ ያነገበ ቃጠሎ ነበር ማለት ነው፡፡ አንደኛውና ዋነኛው በሥርዓቱ የማይፈለጉ ዜጎችን ማደኽት – ሁለተኛው በነሱ ቦታ ደግሞ ለሥርዓቱ ዕድሜ ቀን ከሌት ተንበርክከው ሰይጣንን የሚለምኑ ፍቁራን አባላትንና ደጋፊዎችን ማቋቋም፤ በቃ፡፡ በጨው ደንደስ በርበሬ ተወደስ ይባላል፡፡ በኢትዮጵያ መሬት፣ በኢትዮጵያውያን ሀብትና ንብረት ፀረ-ኢትዮጵያ የሆኑ የመንግሥትን ሞሰብ ገልባጮችና ደጋፊዎቻቸው ይገባበዙበታል፤ ይጠቃቀሙበታል፡፡ እንግዴ ልጅ ሀገር ሻጭ ማዕዱን ሲጫወትበት ልጅ ከበይ ተመልካችነትም ወርዶ የሥቃይ ሰለባ ሆኗል፡፡ እየተራቡ በሀገር መኖርም ክልክል ሆኖ ለሞትና ለስደት መዳረግ ዕጣችን እንዲሆን ተፈርዶብናል፡፡ ይህን ቅሚያና ዘረፋ፣ ይህን የግፎች ሁሉ የበላይ የሆነ ግፍ በእሳት አማካይነት እውን ለማድረግ ደግሞ የኢትዮጵያን መለዮ ለባሽ ይጠቀማሉ -በዓይነቱ ልዩ የሆነ የታሪክ ምፀት ማለት ይህ ነው፡፡ ዋ እኔን! ይህች ቀን ልታልፍ እምቢልታው ሲነፋ እነዚህ ጉግማንጉጎች ምን ይውጣቸው ይሆን?
አዲስ አበባም ውስጥ በትንሹ ሁለት ያህል ቃጠሎዎች በነዚህ ሁለት ቀናት ውስጥ ተከስተዋል፡፡ አንደኛው የብርሃንና ሰላም ማተሚያ ቤት ሲሆን ሌላኛው በአንድ ግለሰብ ቤት የደረሰና የሦስት ሰዎችን ሕይወት የጠየቀ ቃጠሎ ነው፡፡ ያሳዝናል፡፡ ነፍሳቸውን ይማር፡፡ የብርሃንና ሰላም ማተሚያ ቤቱ ግን ያጠያይቃል፡፡ እርግጥ ነው – ቃጠሎው ተፈጥሯዊ ሊሆን ይችላል፡፡ እንደማንኛውም አደጋ ሆን ተብሎ ሳይሆን ድንገት ሊነሳ የመቻሉ ዕድል እንዳለ ሆኖ ከወያኔ ባሕርይ ተነስተን ስንገምት መነሾው ፖለቲካዊ አንድምታም ሊኖረው እንደሚችል ብንጠረጥር “ጠርጣሪዎች(skeptics)” ተብለን ልንታማ አይገባም፡፡ እንዲያውም ስንትና ስንት ጥበቃ የሚደረግለት ትልቅ ድርጅት በቀላሉ ለእሳት ይዳረጋል ብሎ ከማሰብ አለማሰብ ይሻላል ብለን ብንከራከር የሚቻል ይመስለኛል፡፡ ስለሆነም ከድንገቴ አደጋነት ይልቅ የወያኔው ተንኮል እንደሚኖርበት መገመት አይከብድም፡፡ ወያኔ ለምን ብርሃንና ሰላምን ያቃጥላል? ምን ያገኛል? ከመገመት ባለፈ እውነተኛውን ነገር ማወቅ ሊከብድ ይችላል፤ መገመት ደግሞ ለማንም የማይከለከል የሁሉም መብት ነው፡፡

ከሁሉም በፊት ግን አንድ አጠቃላይ እውነት መኖሩን እንመን፡፡ ያም እውነት ወያኔ ቢቻል ቢቻል ኢትዮጵያ እንዳለች ብትቃጠል ወይም እንጦርጦስ ብትወርድ ደስ ይለዋል እንጂ የማይከፋ መሆኑ ነው፡፡ ኢትዮጵያ ስሟ ሲነሳ የሚዘገንናቸውና ጠበል በመጠመቅ ያለ ሰው ላይ እንደተከሰተ ሰይጣን የሚያንዘረዝራቸው እነበረከትንና ሣሞራን የመሳሰሉ መፃጉዕ ዜጎች የሚገኙበት መንግሥታዊ መዋቅር የኢትዮጵያ ታሪክ የሚዘከርበትና አእምሯዊ ቅርስ የሚቀመጥበት ማዕከል ቢቃጠል አይደሰትም ብሎ ማሰብ የዋህነት ይመስለኛል፡፡ በዕንቆቅልሽ ሀገር ውስጥ ልንጠብቅ የማይገባንን ነገር ብንጠብቅ ብልህነት እንጂ ትዝብት ውስጥ ሊያስገባን የሚችል ሞኝነት አይደለም፡፡

በመሆኑም ወያኔ ይህን የእሳት ፖለቲካውን በመጠቀም ዜጎችን ራቁታቸውን ማስቀረቱንና ወደበረንዳ ሕይወት መለወጡን እንዲያቆም፣ የዘመናት ቅርሳችንን እያቃጠለ ታሪክ አልባ ሆነን እንድንቀር ማድረጉን እንዲገታና እስከተቻለ ደግሞ ነፃነታችንን እውን ለማድረግ የምንችልበትን የጋራ ሥልት መቀየስ እንድንችል የጋራ ጥረት እንድናደርግ ጥሪየን አቀርባለሁ፡፡ ሰላም፡፡

↧

[የመልካም አስተዳደር እጦት በወሎ] የዘረፈ፣ እግር የቆረጠ፣ ሕዝብን በጥይት እየገደለ ያለ ስልጣን ላይ ሆኖ ይንደላቀቃል

$
0
0

(የሰሜን ወሎ ሕዝብ በገበያ ላይ - ፎቶ ፋይል)

(የሰሜን ወሎ ሕዝብ በገበያ ላይ – ፎቶ ፋይል)


ለዘ-ሐበሻ ድረ ገጽ አዘጋጆች
ክቡር ሰላምታየ ይድረሳችሁ

ከዚህ በመቀጠል የዘወትር የፕሮግራምችሁ ተከታታይ ስሆን ይህን የመልካም አስተዳደር ችግር አየር ላይ እንድታውሉልኝ እየጠየኩ እን ሁልግዜው ለሁሉም የምታቀርቡትን አስተያየት ሙያችሁ በሚፈቅደው መሠረት እንደምታቀርቡልኝ ወይም አየር ላይ እንደምታውሉልኝ በመተማመን ነው፡፡
በሰሜን ወሎና ዞን በሀብሩ ወረዳና በመርሳ ከተማ እንደማንኛውም የኢትዮጵያ አካባባቢ በየግዜው የሚስተዋሉት የመልካም አስተዳደርና የሙስና ችግሮች ነዋሪውን የከተማና የገጠር ህዝብ እግር ተወርች ሰቅለው ይዘውታል፡፡ ለየት የሚያደርገው ነገር ቢኖር ከመንግስት ደቀመዛሙርት መሰል ሚዲያዎች የምንተነፍስበት ወይም ሃሳባችንን የምንገልፅበት አማራጭ አለመኖሩ ነው፡፡ ይህም የናንተ የዘገባ አድማስ ሁሉንም አካባቢዎች የሚሸፍን አለመሆኑ ይመስለኛል ፡፡

ከዚህ በተረፈ ጉዳዩ አዲስና ልዩ ባይሆንም ድግግሞሽና አንደኛው ከሌለኛው ሲነፃፀር በጣም የከፋ እየሆነ በመምጣቱ ነው፡፡ በዚህም ምክንያት አቤቱታው በምድር ላይ ያሉት ቱባ ባለስልጣኖች ጆሮ ነፊውን በየእምነቱ በፈጣሪው መፀለይ እና አቤት ለማለት ተገዷል እናም የናንተ የአቀራረብ ብስለት ታክሎበት መልዕክቱን ለአየር ታውሉልኛላችሁ ብዩ ተስፋ አደርጋለሁ ፡፡
መቸም የመልካም አስተዳደር ጉዳይ ሲነሳ ተነግሮ አያልቅም ነገር ግን ቀደም የተፈፀመው በደል ላያንሰው አዳዲስና ከፀሐይ ጋር አብረው ብቅ የሚሉት የትም የለሉ ቢሆንም የቅርቡን ለመግለፅ ያህል
1. በመርሣ ከተማ አስተዳደር ነዋሪ የሆኑ 35 /ሰላሳ አምስት/ መንጃ ፈቃድ ያላቸው ነዋሪዎች በአማራ ክልል በቅርቡ እንዳያወጡ በመከልከላቸውና

ሙስና የበዛበት አሰራር ስላለ ወደ ተሻለውና አገሪቱን በበላይነት ወደ ሚመራው ክልል 1 ህዝባዊ ወያኔ ሀርነት ትግራይ በመሄድ መንጃ ፈቃድ አውጥተው አሁን በከተማው የትግራይ ክልል መንጃ ፈቃድ አማራ ክልል ላይ አይሰራም በማለት ታግደዋል ፡፡ ክልሉ በማንና በምን እንደሚመራ ካለመታወቁም በላይ የወያኔን መሪነት ብአዴን መካዱ ይሆን ወይስ በአንድ አገር ሁለት ዓይነት ህግ መኖሩ ነው መልስ ያጣ ጉዳይ ሆኗል፡፡

2. በዚሁ በመርሣ ከተማ ዙሪያዋን በሚገኙ ወደ ከተማ የተከለሉ ቀበሌዎች ነዋሪ የሆኑ አራሽ ገበሬ ለፍቶና ጥሮ ለአመታት ጥሪቱን በሚያስጨርስ ሁኔታ የሰራውን ቤት ለምሳሌ አቧሬ አካባቢ የአቶ ሙመድ ሰይድ ቤት 8X9 የሆነ ቤት አገልግሎት በማይሰጥ መልኩ አፍርሰው ወደ ሌሎች መሰል ግለሰቦች ሲገቡ ነዋሪው ህዝብ በነቂስ ወጥቶ ባለስልጣኖቹን በመፈታተኑ እንዲባረሩ አድርጓቸዋል፡፡ በሌላ በኩል በ25/6/2006 ዓ.ም ከጠዋቱ 4፡30 /አራት ሰዓት ተኩል / አካባቢ በዚሁ ከተማ ልዩ ቦታው መልካጨፌ ከተባለው አካባቢ የ8 /ስምንት/ ሰው አርሶ አደር ቤት አፍርሰው ወደቀጣዩ ሲሸጋገሩ ጉዳዩ ያበሳጨው ነዋሪ ህዝብ ከአንድ መቶ በላይ የሚቆጠር ፖሊስ ፣ሚሊሻ አመራር በመሆን ህዝቡ በአመፅ በመነሳት ከሃምሳ በላይ ጥይት ተተኩሶ ሁለት ግለሰብ አርሶ አደሮች የህዝብ ተወካይ ነን በሚሉ ታጣቂዎች ተመትተው ቆስለው ህክምና ላይ ሲገኙ የጣፋው ጠፍቶ ቀሪውን በትግል ማዳን ችሏል ይሁንና መብቱን መገፋቱ ሳያንሰው ብሎም በቤት ውስጥ የነበሩ መንታ የወለደች ሴት ሜዳላይ እንድትወድቅ ተደርጓል ድርጊቱን ለምን ተከላከላችሁ ተብለው ሁከት ፈጣሪ በመባል ማረሚያ ቤት ገብተው ይገኛሉ ፡፡ ቀሪዎቹ ነዋሪዎች የተተኮሰውን ጥይት ዋጋ እንዲከፍሉ ተጠይቀዋል፡፡ ይህ የህዝብ ወገናዊነት ወይስ ምን ይሉታል ?

3. የህዝብን ሀብትና ንብረት ስልጣናቸውን ተጠቅመው የከበሩ የወረዳ አመራሮች ከመጠየቅ ይልቅ ወደ ፓርላማ እንዲገቡ ለከፍተኛ ትምህረት ተቋም ዕድል ተጠቃሚ እንዲሆኑ መሬት በሽልማት የሚሰጥበት ለህገ-መንግስቱ መሬት መሸጥ መለወጥ ላሳር የተባለበትን ለካቢኔ በሽልማት የሚሰጥበትን ሁኔታ ሲኖር ከዚህ እንደሚቀጥለው ይሆናል

ለአብነት ያክል፡-
• የቁጥር 27 ቀበሌን የገበሬውን መሬት የሸጡ ወይም እንዲሸጥ በቃለ ጉባዔ የያዙ የከፍተኛ ትምህርት ተጠቃሚ እንዲሆኑ ሲበረታቱ የቀበሌው አስተዳዳሪ ግን በ9/ዘጠኝ/ አይነት ክስ ተከሶ ማረሚያ ቤት ይገኛል

• በተጨማሪ11/አስራ አንድ ቤት /ያቃጠለ የአንድ ሰው እግር የቆረጠ ይባስ ብሎ በዚሁ ድርጊቱ ሳይበቃው ከሌላ የካቢኔ ጓደኛው ጋር በመሆን በሽጉጥ ከስደት ተመላሽ የሆነን ግለሰብ በሴት ምክንያት ጠግቦ አደሮች እጁ ላይ ተመትቶ በሆስፒታል በመረዳት ላይ ሲገኝ ይህ ሳያንስ ቤተሰቦቹ ተለቅመው እንዲታሰሩ ተደርጎ ሲቀጡ ጉዳዩን የፈፀሙት ባለስልጣኖች እድሜ ለስልጣን ብለው ሌላውን ባለተራ የጥይት ማረፊያቸውን ይጠብቃሉ።

4. የወረዳው አመራር /የሀብሩ ወረዳ ማለቴ/ ነው ከክልል በመጣ የኦዲት ባለሙያ በተረጋገጠው መሠረት አንድ አመራር ከ44 – 75 ሽህ ብር ከ365 ቀን በላይ በውሎ አበልና መሰል የወጭ ዘዴ ተጠቅሞ ከህግ ውጭ ማድረጋቸው ስለተረጋገጠ የክልሉ ኦዲተር ሪፖርት ቀርቦ እያለ እስካሁን ድረስ በህግ ፊት ሁሉም ሰው እኩል ነው የሚባለውን በነሱ ላይ ስለማይሰራ በፍታብሄርም ሆነ በወንጀል እንዳይጠይቁ ጠያቂና ተጠያቂ ጠፍቶ የአገር ሀብት ባክኖ ቀርቷል፡፡ አቤት የሚባልበት ቦታ ጠፍቷል ፡፡

5. ከዚህ በላይ የተዘረዘሩት ጉዳዮች ማለትም የገጠር ወረዳውና የከተማ አስተዳደሩ የሚፈፅማቸውን አላግባብ የሆኑ አሰራሮች መከታተልና መቆጣጠር የተፈፀመውንም ሆነ ችግሮች እንዳይፈፀሙ መከላከል ሲገባቸው ይባስ ብለው የወረዳው ፍ/ቤት ሰብሳቢ ዳኛ ከዳኝነት ነፃ የሆነው እንኳ ሳይቀር የፍትህ ጽ/ቤት ኃላፊ ካቢኔ ተብየው እነዚህ አመራሮችና ሙሰኞች በህግ እንዳይጠየቁ ምርመራ ሲጀመር ከዞን ጀምሮ ምርመራ እንዲቋረጥ እየተደረገ የዳኝነት ነፃነት በሚጋፋ መልኩ በህግ ፊት ሁሉም ሰው እኩል ነው ተብሎ በህገ-መንግስቱ አንቀጽ 25 ላይ በግልፅነት ተቀምጦ እያለ ለአመራር /ተሿሚ / ህጉ የማይሰራበት ለሌች ዜጎች ግን ተተንትኖና ተዘርዝሮ የሚሰራበት ወረዳ በመሆኑ ህግ አልባነት ወይስ ህግ የተላበሰ አሰራር ይህን ሁሉም መልሶ አጥቶበታል።

በአጠቃላይ በከተማችንና በወረዳችን ያለውን የመልካም አስተዳደር ችግር የሰዎች ሰብዓዊ መብት አለመከበር ድብደባ ዛቻና ማስፈራራት በመጠቀም ስልጣናቸውን ለማራዘም ከላይ ታች የሚባዝኑ ስለሆነ ለሀገርም ሆነ ለህዝብ የማይጠቅም በመሆኑ ይህነን አስነዋሪ የ21ኛው ክፍለ ዘመን የማይመጥንና የማይገልጽ ነውር ተግባር በህዝቡ ስምና በራሴ ስም ለአየር ይበቃ ዘንድ መልካም ትብብራችሁን ከአክብሮት ጋር እንደማትነፍጉኝ በመተማመን አቀርባለሁ፡፡
የዘወትር አንባቢያችሁ ይነበብ ታምሩ
ከመርሳ ከተማ

ጉለቶቹን ለማጣራት ካስፈለገ ስልክ የከተማ አስተዳደሩ
ከንቲባ ስልክ 0921522287
የገጠር ወረዳ አስትዳደር ስልክ 0333330007(49)
የገጠር ፖሊስ ስልክ 03333300022(21) ክፋታቸው ካልበረታ ማገኘት ይቻላል፡፡

↧

መታመን በቀድሞ ነው !! (ዳንኤል ፍቅሬ)

$
0
0

ዳንኤል ፍቅሬ

የሰሞኑ የኪዌት ጉዳይ ሁላችንንም እያነጋገረ ያለ ጉዳይ ነው በተለይ በቅርቡ ከሳውዲ አረብያ የችግር ትኩሳት ትንሽ መብረድ ጋር ተያይዞ  በኪዌት የባለ ስልጣን ልጅ መገደል የወገኔን ችግር   ያብስዋል ብዬ  ነገሩን ትኩረት ሰጥቸው  እየተከታተልኩ ነው :: በጣም ትኩረቴን የሳበው እና የታዘብኩተ  የኪዌት የፓርላማ አባላት ተወያይተው የወሰኑት ጉዳይ ነው ::

The lawmaker stressed the need to oblige housemaids to undergo tests regularly to ensure they are not suffering from any psychological illness. 

.የቤት ውስጥ ሰራተኞች ቅጥር ውደ ኪዌት ሲመጡ የአምሮአቸው ሁኔታ ይጠና ማለታቸው ትክክል ቢሆንም እኔ ግን በትዝብት እና በግርምት ነው የተመለከትኩተ :: ምነው ስንቱን ወገኖቻችንን ሲገድሉ ሲያርዱ ሲያንገላቱ የነሱን የራሳቸውን  አእምሮ ሁኔታ አለማጤናቸው ?? እውነት ትክክል የሆነና ያልሆነ  ነገር ለካ እንደ ሃገሩ ይለያያል እነሱ ሲፈጽሙት እና እኛ ስንፈጽመው የሚሰጠን ስያሜ ለየቅል ነው ለካ :: በአረቡ አለም ስንት ህሊናን የሚያስትና እሚያንገፈገፍ ዘግናኝ ግፍ ተፈፅሞብን እንዳለፈ ቤቱ ይቁጠረው እውነቱን ነው ትልቁ መጽሓፍ ያለው ” በራስክ ውስጥ ያለውን ትልቁን ምስሶ የሚአክል ጉድፍ እያለ የወንድምክን ትንሽዋን የአይን ጉድፍ ላውጣ ማለቱ …………” የሚለው  የሚስማማቸው ይመስለኛል::

            ያገራችን  መንገስትም ለአንድ ዜጋው የሚሰጠው  ክበር ሰለሌለ የሚከፍለው ዋጋ የዛኑ ያህል የከፋ ነው:: አንድ ዜጋ በሚፈጥረው ችግር ህብረተሰበን ብሎም አገርን እንደሚጎዳ በቅጡ የተገነዘበው አልመሰለኝም እኔ ሳስበው ችግሩ ሁላችንንም ያካትታል በተለይ መንግስትን!!! ” ምቼም መንግስት የሚታመነው በባለፈው ስራው ነው” በተለይ አረብ አገር ባሉ ዜጎቻችን ላይ ሲበደሉ  ሲገደሉ መሬት ለመሬት ሲጎትቱአቸው አሁን ያለው መንግስት ለወገኑ ጥብቅና ሲቆም ሲታገልላቸው መብታቸውን ለማስከበር ደፋ ቀና ሲል አላየንም ከነሱ ጋረ ሆኖ በችግራችን ላይ ችግር ሲጨምርብን እንጂ !!  በየሃገሩ ተበትነው ያሉ ዜጎቻችን አለሁ የሚል  መንግስት ወገን ከሌለ ምኑን መንግስት ሆነልን!!  አገር ውሰጥም ተገብቶ ጭቆናወና ችግሩ እየቀጠለ የሚሄድ ከሆነ አሁንም እንዳየነው ፍልሰቱ መቀጠሉ የማይቀር ነው :: በቅርቡ ከሳውዲ የተመለሱት ወዳገራቸው ገብተው በያቅጣጫው ወደ ውጭ  የተበተኑት ይሄ ያደባባይ ሚስጥር ነው :: እና ለዚች ወገናችን  ከተብደለችው አንጻር ፍርድዋ እንዲቀልላት በጎ አደራጊ ደረጅቶች ወይ ገለሰብ እንድረስላት ::

 

↧

ሁለተኛውን ዙር የሚሊየኖች ድምጽ እንቅስቃሴን በመደገፍ: ላስ ቬጋስ የአዲስ አበባዉን – አትላንታዎች አዋሳን -ዴንቨሮች ደሴን –ቃሌ እና ደብተራው ቁጫንና ድሬደዋን ስፖንሰር አደረጉ !

$
0
0

ሚሊየነች ድምጽ – ላስ ቬጋስ የአዲስ አበባዉን የመጀመሪያ ስብሰባ ስፖንሰር አደረገች!

የሚሊዮኖች ድምጽ ንቅናቄ በአገሪቷ ዉስጥ ባሉ አሥራ ሰባት ከተሞች፣ ሕዝባዊ እንቅስቃሴዎች እንደሚያደርግ ይፋ ማድረጉ ይታወቃል። እንቅስቃሴ በአዲስ አበባ ሕዝባዊ ስብሰባ በማድረግ የሚጀመር ሲሆን፣ በሌሎች ከተሞች ከአንድነት ጽ/ቤቶች ወደ አደባባይ በሚሄድ ትይንተ ሕዝቦች ይደረጋሉ።Las Vegas1

ላስ ቬጋስ፣ ኔቫዳ፣ ከአዲስ አበባ ጋራ ሶሊዳሪቲ በመመሰረት ፣ በዚያ የሚገኙ ኢትዮጵያዉያን፣ በአዲስ አበባ ለሚደረገዉ ሕዝባዊ ስብስበ የሚያስፈልገውን ወጭ ሙሉ ለሙሉ ለመሸፈን የተዘጋጁ ሲሆን፣ «ከሚሊዮኖች አንዱ ነን» እያሉም ነው።

ይህ የሚሊየነሞች እንቅስቃሴ የአንድ ፓርቲ እንቅሳቅሴ ብቻ ሳይሆን የኢትዮጵያ ሕዝብ እንቅስቃሴ እንደመሆኑ፣ በአገራችን ዴሞክራሲና የስርዓት ለዉጥ እንዲመጣ የሚፈልጉ ዜጎች ሁሉ ሊቀላቀሉት፣ ሊደግፉት፣ የራሳቸው ሊያደርጉት የሚገባ እንቅስቃሴ ነዉ። ይህ እንቅስቃሴ የሚሊዮኖች እንቅስቃሴ ነው። የእያንዳንዳችን እንቅስቃሴ ነው።

በዳያስፖራ የሚሊየነሞች ግብረ ኃይል፣ በላስ ቬጋስ ያሉ ኢትዮጵያዉን ላሳዩት አኩሪና ኢትዮጵያዊ እንቅስቃሴ ያለዉን አድናቆት እየገለጸ፣ በሌሎች ከተሞችም የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን እራሳቸውን እያደራጁ ፣ አገር ቤት ከፍተኛ መስዋእትነት እየከፈለ ካለው ሕዝብ ጎን እንዲቆሙ፣ ትግሉን እንዲቀላቀሉና ከሚሊዮኖች አንዱ እንዲሆኑ ጥሪ ያቀርባል።

በምትኖሩበት ከተማ ተደራጅታችሁ፣ ከዚህ ግብረ ኃይል ጋር በመስራት በአገር ቤት የሚደረጉ እንቅስቃሴዎችን ስፖንሰር ማድረግ የምትፈልጉ፣ በሚከተሉት አድራሻ ሊያገኙን ይችላሉ።

ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር !

millionsforethiopia@gmail.com
404- 518-7858

 

የሚሊዮኖች ድምጽ – አትላንታዎች ከአዋሳ ጎን በመቆም የሚሊዮኖች አንዱ ሆኑ !

የሚሊዮኖች ድምጽ ንቅናቄ በአገሪቷ ዉስጥ ባሉ አሥራ ሰባት ከተሞች፣ ሕዝባዊ እንቅስቃሴዎች እንደሚያደርግ ይፋ ማድረጉ ይታወቃል። እንቅስቃሴ በአዲስ አበባ ሕዝባዊ ስብሰባ በማድረግ የሚጀመር ሲሆን፣ በሌሎች ከተሞች ከአንድነት ጽ/ቤቶች ወደ አደባባይ በሚሄድ ትይንተ ሕዝቦች ይደረጋሉ።

አትላንታ ጆርጂያ ከአዋሳ ከተማ ጋር ሶሊዳሪቲ በመመሰረት ፣ በአዋሳ የሚገኙ ኢትዮጵያዉያን በሚሊዮኖች ድምጽ ዘመቻ በከተማቸው ለሚያደርጉት እንቅስቃሴ የሚያስፈልገውን ወጭ ሙሉ ለሙሉ ለመሸፈን የተዘጋጁ ሲሆን፣ አትላንታዎች  «ከሚሊዮኖች አንዱ ነን» እያሉ ነው።

Atlantaይህ የሚሊየነሞች እንቅስቃሴ የአንድ ፓርቲ እንቅሳቅሴ ብቻ ሳይሆን የኢትዮጵያ ሕዝብ እንቅስቃሴ እንደመሆኑ፣ በአገራችን ዴሞክራሲና የስርዓት ለዉጥ እንዲመጣ የሚፈልጉ ዜጎች ሁሉ ሊቀላቀሉት፣ ሊደግፉት፣ የራሳቸው ሊያደርጉት የሚገባ እንቅስቃሴ ነዉ። ይህ እንቅስቃሴ የሚሊዮኖች እንቅስቃሴ ነው። የእያንዳንዳችን እንቅስቃሴ ነው።

በዳያስፖራ የሚሊየነሞች ግብረ ኃይል፣ በአትላንታ ያሉ ኢትዮጵያዉን ላሳዩት አኩሪና ኢትዮጵያዊ እንቅስቃሴ ያለዉን አድናቆት እየገለጸ፣ በሌሎች ከተሞችም የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን እራሳቸውን እያደራጁ ፣ አገር ቤት ከፍተኛ መስዋእትነት እየከፈለ ካለው ሕዝብ ጎን እንዲቆሙ፣ ትግሉን እንዲቀላቀሉና ከሚሊዮኖች አንዱ እንዲሆኑ ጥሪ ያቀርባል።

እስካሁን የላስ ቬጋስ ኢትዮጵያዉያን የመጀመሪያዉን የአዲስ አበባ እንቅስቃሴ፣ የቃሌ ፓልቶክ ክልፍ በደቩብ ክልል ቁጫ የሚደረገዉ እንቅስቃሴ፣ የደብተራዉ ፓልቶክ ክፍል ደግሞ አንጋፋዋን ድሬዳዋ ስፖንሰር እንደሚያደርጉ ማሳወቃችን ይታወሳል።

በምትኖሩበት ከተማ ተደራጅታችሁ፣ ከዚህ ግብረ ኃይል ጋር በመስራት በአገር ቤት የሚደረጉ እንቅስቃሴዎችን ስፖንሰር ማድረግ የምትፈልጉ፣ በሚከተሉት አድራሻ ሊያገኙን ይችላሉ።

ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር !

millionsforethiopia@gmail.com

404- 518-7858

 

 

የሚሊዮኖች ድምጽ – ዴንቨሮች ከደሴ ጎን በመቆም የሚሊዮኖች አንዱ ሆኑ !

የሚሊዮኖች ድምጽ ንቅናቄ በአገሪቷ ዉስጥ ባሉ አሥራ ሰባት ከተሞች፣ ሕዝባዊ እንቅስቃሴዎች እንደሚያደርግ ይፋ ማድረጉ ይታወቃል። እንቅስቃሴ በአዲስ አበባ ሕዝባዊ ስብሰባ በማድረግ የሚጀመር ሲሆን፣ በሌሎች ከተሞች ከአንድነት ጽ/ቤቶች ወደ አደባባይ በሚሄድ ትይንተ ሕዝቦች ይደረጋሉ።

Denverዴንቨር ኮሎራዶ ከደሴ ከተማ ጋር ሶሊዳሪቲ በመመሰረት ፣ በደሴ የሚገኙ ኢትዮጵያዉያን በሚሊዮኖች ድምጽ ዘመቻ በከተማቸው ለሚያደርጉት እንቅስቃሴ የሚያስፈልገውን ወጭ ሙሉ ለሙሉ ለመሸፈን የተዘጋጁ ሲሆን፣ አትላንታዎች  «ከሚሊዮኖች አንዱ ነን» እያሉ ነው።

ይህ የሚሊየነሞች እንቅስቃሴ የአንድ ፓርቲ እንቅሳቅሴ ብቻ ሳይሆን የኢትዮጵያ ሕዝብ እንቅስቃሴ እንደመሆኑ፣ በአገራችን ዴሞክራሲና የስርዓት ለዉጥ እንዲመጣ የሚፈልጉ ዜጎች ሁሉ ሊቀላቀሉት፣ ሊደግፉት፣ የራሳቸው ሊያደርጉት የሚገባ እንቅስቃሴ ነዉ። ይህ እንቅስቃሴ የሚሊዮኖች እንቅስቃሴ ነው። የእያንዳንዳችን እንቅስቃሴ ነው።

በዳያስፖራ የሚሊየነሞች ግብረ ኃይል፣ በዴንቨር ያሉ ኢትዮጵያዉን ላሳዩት አኩሪና ኢትዮጵያዊ እንቅስቃሴ ያለዉን አድናቆት እየገለጸ፣ በሌሎች ከተሞችም የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን እራሳቸውን እያደራጁ ፣ አገር ቤት ከፍተኛ መስዋእትነት እየከፈለ ካለው ሕዝብ ጎን እንዲቆሙ፣ ትግሉን እንዲቀላቀሉና ከሚሊዮኖች አንዱ እንዲሆኑ ጥሪ ያቀርባል።

እስካሁን የላስ ቬጋስ ኢትዮጵያዉያን የመጀመሪያዉን የአዲስ አበባ እንቅስቃሴ ስፖንሰር ያደረጉ ሲሆን፣ የአትላንታ ኢትዮጵያዉያን በአዋሳ፣ የቃሌ ፓልቶክ ክልፍ በደብብ ክልል ቁጫ፣ የደብተራዉ ፓልቶክ ክፍል ደግሞ በአንጋፋዋ በድሬዳዋ የሚደረጉ እንቅስቃሴዎች ስፖንሰር እንደሚያደርጉ ማሳወቃችን ይታወሳል።

በምትኖሩበት ከተማ ተደራጅታችሁ፣ ከዚህ ግብረ ኃይል ጋር በመስራት በአገር ቤት የሚደረጉ እንቅስቃሴዎችን ስፖንሰር ማድረግ የምትፈልጉ፣ በሚከተሉት አድራሻ ሊያገኙን ይችላሉ።

 

ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር !

millionsforethiopia@gmail.com

404- 518-7858

 

 

የሚሊዮኖች ድምጽ – ቃሌ እና ደብተራው ቁጫንና ድሬደዋን ስፖንሰር አደረጉ !

በደቡብ ክልል፣ በጋሙ ጎፋ ዞን የምትገኝ ወረዳ ናት። ወደ 150 ሺህ የሚጠጋ ነዋሪ አላት። በዚያ ያሉ ገበሬዎች ከሚያርሱበት ቦታ በግድ እንዲፈናቀሉ ከመደረጉ በተጨማሪ፣ ብዙዎች ያታሰሩባት ወረዳ ናት። የቁጭ ወረዳ ትባላለች።

dire_kucha-1በአንድነት ፓርቲ አነሳሽነት ለሕዝብ የፋ የሆነው የሚሊዮኖች ድምጽ ለመሬት ባለቤትነት ትኩረት ከሰጠባቸው ወደ አሥራ የሚሆኑ አካባቢዎች አንዷ ቁጫ ናት። በቁጫ ሊደረግ የታሰበዉን ትእይነተ ሕዝብ በመደገፍ፣ በዚያም ለሚኖረው የተገፋዉ ሕዝብ ሶሊዳሪቲ በማሳየት የቃሌ ፓልቶክ ክፍል ፣ የቁጫን እንቅስቃሴ ሙሉ ለሙሉ እንደሚሸፍን እና ስፖንሰር እንደሚያደርግ ይፋ አደርጓል።
ሌላዋ የሚሊይን ድምጽ ዘመቻ የሚደረግባት ከተማ፣ የኢትዮዮጵያ ሁለተኛ ከተማ የሆነችዋ አንጋፋዉ ድሬዳዋ ናት። የደብተራዉ ፓል ቶክ ክፍል ፣ ድረደዋን ስፖንሰር እንደሚያደርግም ለማወቅ ተችሏል።

የቃሌ እና የደብተራዉ ፓል ቶክ ክፍሎች ከአለም ዙሪያ ሁሉ የተሰባሰቡ ፣ በኢንተርኔት ፓልቶክ አፕሊኬሽን ፣ በአገራቸው ጉዳይ ላይ ዘወተር የሚመካከሩ፣ የአገራቸው ጉዳይ የሚያስጨንቃቸው ኢትዮጵያዊያን የተሰባሰቡበት ክፍሎች ነው።

በኢትዮጵያ የሚደረገዉ ሰላማዊ ትግል፣ ስለተመኘንና ስላወራን ብቻ ዉጤት የሚያመጣ አይደለም። አገዛዙ ዘወትር ስለሚፈጽማቸው ግፎች ማዉራት አንድ ነገር ነው። እነዚህ ግፎች እንዲያቆሙና የስርዓት ለዉጥ እንዲመጣ ማድረግ ሌላ ነገር ነው።

የቃሌና የደብተራው ታዳሚዎች ፣ ከዉይይት አልፈው፣ አገር ወዳድነታቸውን በተግባር በማሳየት፣ በሜዳ ፊት ለፊት አምባገነንነትን እየተጋፈጡ ያሉ ጀግኖችን በቁጫና በድሬደዋ በመደገፍ የሚሊዮኖች አንዱ ነን እያሉ ነው።

የቃሌና የደብተራዉ ፓልቶክ ክፍሎች ለወሰዱት አኩሪና አገር ወዳድ አቋም ያለንን አድናቆት እየገለጽን፣ የተቀረነዉ በየአካባቢያችን እየተሰባሰብን ትግሉን እንድንቀላቀል፣ከሚሊዮኖች አንዱ እንሆን ዘንድ ጥሪ እናቀርባለን።

ትግሉን ለመርዳት፣ ለመደገፍ፣ ከሚሊዮኖች አንዱ ለመሆን የምንፈልግ ካለን በሚከተለው አድራሻ ሊያገኙን ይችላሉ።

ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር !

millionsforethiopia@gmail.com

↧
↧

የተቃዋሚዎች ኅብረት የድል ዋስትና ነው

$
0
0
↧

ወደ እስራኤል ለመሄድ ቪዛ የጠየቁ ጉዟቸውን እንዲያራዝሙ ኢምባሲው አስታወቀ

$
0
0

Israel Flag
ለጉብኝትና ለሥራ ወደ እስራኤል የሚጓዙ ኢትዮጵያዊን አዲስ አበባ ከሚገኘው የእስራኤል ኤምባሲ የቪዛ አገልግሎት ማግኘት አለመቻላቸውን ለሰንደቅ ጋዜጣ ገለፁ።

አዲስ አበባ የሚገኘው የእስራኤል ኤምባሲ ለሰንደቅ እንደገለፀው፤ ወደ እስራኤል ለጉብኝት የሚጓዙ ኢትዮጵያዊያን ላልተወሰነ ጊዜ ጉዟቸውን እንዲያራዝሙ አሳስቧል። የቪዛ አገልግሎት የሚያገኙት የቡሩንዲ እና የሩዋንዳ ዜጎችንም ጉዟቸውን እንደሚያስተጓጉል ለማወቅ ተችሏል።
ኤምባሲው አያይዞ እንደገለጸው፤ በእስራኤል መንግስት እና በእስራኤል ዲፕሎማቶች መካከል የደሞዝና የጥቅማጥቅም ጭማሪ አስመልክቶ የተነሳው ውዝግብ እልባት እስከሚያገኝ የዲፕሎማሲና የቪዛ አገልግሎት እንደማይሰጥ አስታውቋል።

የእስራኤል ዲፕሎማቶች ከማርች 5 ቀን 2014 ጀምሮ የመቱትን የስራ ማቆም አድማ ተከትሎ በዓለም የሚገኙ የእስራኤል ኤምባሲዎች፣ ከእስራኤል መንግስት ባለስልጣናት፣ ተቋማት፣ ግብረ ሰናይ ደርጅቶች፣ አርቲስቶች እና ከሌሎቹም ጋር ምንም አይነት ግንኙነት አቋርጠዋል።

አዲስ አበባ የሚገኘው የእስራኤል ኤምባሲ ቃል አቀባይ የሆኑት ሊዮ ቪኖቨስኪ ስለተፈጠረው አለመግባባት አነጋግረናቸው በሰጡን ምላሽ ፣ “ለእስራኤል በተለያዩ የስራ መስኮች እየሰራን እንገኛለን። ስለዚህም በዓለም ዓቀፍ ተቀባይነት ባለው ደረጃ ደሞዛችን መስተካከል አለበት። በሌሎች ሀገሮች የዲፕሎማሲ ስራዎች የብሔራዊ ጥቅም ማስከበሪያ ማገሮች ተደርገው ነው የሚወሰዱት፣ ለእኛም በዚህ ደረጃ ሊስተካከልልን ይገባል። ዲፕሎማት በመሆናችን በድርድር እናምናለን። በሌላ ወገን ግን ለመነጋገር ፍቃደኛ ካልሆኑ ውጤቱ ግልፅ ይመስለኛል። ስለዚህም ሚኒስትር ላፒድ እና የስራ ባልደረቦቻቸው መንቃት አለባቸው። ምክንያቱም እኛ የወሰድነው እርምጃ፣ የማንቂያ ጥሪ ነው” ብለዋል።

በእስራኤል ውስጥ እና ውጪ የሚገኙ 1200 ዲፕሎማቶች ለድርድር መንግስታቸውን የጋበዙ ቢሆንም የእስራኤል የውጪ ጉዳይ ሚኒስትር መስሪያቤት ድርድሩን አስመልክቶ የሰጠው መግለጫ የለም።

↧

ነገረ ኢትዮጵያ ቁጥር – 5 ቁልፍ አገራዊና ወቅታዊ ጉዳዮችን ይዛ እነሆ በPDF ያንብቧት

$
0
0
↧

ድምፃዊ ስንታየሁ ጥላሁን-ሂቦንጎ

$
0
0


‹‹ሂቦንጎ›› የወቅቱ ተወዳጅ ዘፈን ነው፡፡ ይህንን ዘፈን የተጫወተው ደግሞ ድምጻዊ ስንታየሁ ጥላሁን ነው፡፡ በ1973 ዓ.ም እዚህ አዲስ አበባ የተወለደው ስንታየሁ የቤተሰቡ የመጀመሪያ ልጅ ሲሆን፣ ከእሱ በታች አራት ልጆች አሉ፡፡ እስከ ስምንተኛ ሆሳዕና ውስጥ፣ ከዘጠነኛ እስከ አስራ ሁለተኛ ክፍል ደግሞ እዚህ አዲስ አበባ ውስጥ በጥቁር አንበሳ ት/ቤት ነው የተማረው፡፡
‹‹ሂቦንጎ›› የሚለው ዘፈን በሙያው አፍቃሪ ዘንድ ከፍተኛ ተቀባይነት ማግኘቱ ምክንያት ሆኖን ነው ከድምፃዊ ስንታየሁ ጥላሁን ጋር ቃለ-ምልልስ ያደረግነው፡፡ መልካም ንባብ፡፡
ዘሃበሻ፡- ድምፃዊ ስንታየሁ ጥላሁን ከሁሉ በማስቀደም ይህንን ቃለ ምልልስ ለመስጠት ፈቃደኛ በመሆንህ አመሰግናለሁ፡፡

// ]]>
ስንታየሁ፡- እኔም እድሉን ስለሰጣችሁኝ ከልብ ነው የማመሰግነው፡፡
ዘሃበሻ፡- ስንታየሁ ጥላሁን ራሱን አጭር በሆነ ሁኔታ ያስተዋውቅ ተብሎ ቢፈቀድልህ ምን ብለህ ታስተዋውቃለህ?
ስንታየሁ፡- እኔ የተወለድኩት እዚሁ አዲስ አበባ ከፍላሚንጎ ጀርባ ነው፡፡ ትንሽ ልጅ ሆኜ ወደ ሆሳዕና ሄድኩኝ፡፡ ስለዚህ ያደኩት ሆሳዕና ነው ማለት ነው፡፡ ያደኩት ደግሞ በአያት እጅ ነው፡፡ ሆሳዕና ምንም አይነት የሙዚቃና የቴአትር ክበባት አልነበሩም፡፡ የሙዚቃ ፍቅሩ ግን ውስጤ ነበር፡፡ ሁል ጊዜ ቤት ውስጥ እዘፍናለሁ፡፡ ድምፄን የሚሰሙ ሰዎች መዝፈን እንደምችል ሲነግሩኝና ሲያበረታቱኝ ወደ አዲስ አበባ መጣሁኝ፡፡
ዘሃበሻ፡- መቼ ነበር ወደ አዲስ አበባ የመጣኸው?
ስንታየሁ፡- 1991 ዓ.ም መጨረሻ ላይ ነው የመጣሁት፡፡ በ1982 ዓ.ም መጨረሻ ላይ አዲስ ከተማ ወወክማ በክረምት የሚሰጥ የሙዚቃ ስልጠና ነበር፡፡ ስልጠናውን ከጀመርኩ በኋላ እዛም ጥሩ ነገር እንዳለኝ ተነገረኝ፡፡ በጊዜው ወደ ሁለት መቶ የምንጠጋ ልጆች ነበርን ስልጠናውን እንወስድ የነበረው፡፡ እኔ አንደኛ ነበር የመጣሁት፡፡
ዘሃበሻ፡- ምን ነበር የሚሰጣችሁ ስልጠና?
ስንታየሁ፡- ስለ ድምፅ እንማር ነበር፡፡ ውዝዋዜም ሁሉ ሞክሬያለሁ፡፡ በቡድን በቡድን ተከፋፍለን ውዝዋዜ ሁሉ አቅርበን ነበር፡፡ ከዚያ ወደ ድምፅ ገባሁ፡፡
ዘሃበሻ፡- ከኢትዮጵያ የሙዚቃ አፍቃሪ ጋር ያስታወቀህ ‹‹ሂቦንጎ›› የሚለው ዘፈን ነው፡፡ ‹‹ሂቦንጎ›› ምን ማለት ነው?
ስንታየሁ፡- ሂቦንጎ ማለት ወንዶችና ሴቶች በቡድን ሆነው የሚዘፍኑት ዘፈን ነው፡፡
ዘሃበሻ፡- የሚዘፈንበት የተለየ ወቅት አለው?
ስንታየሁ፡- የተለየ ወቅት የለውም፡፡ ሠርግ ላይ ሊሆን ይችላል፣ አራስ ቤት ሊሆን ይችላል፣ የግርዛት በዓልም ላይ ሊሆን ይችላል ግን ወንዶችና ሴቶች በቡድን፣ በቡድን ሆነው የሚሞጋገሱበት፣ የሚተቻቹበት፣ የሚወራረፉበት፣ ብሎም የከንፈር ወዳጅነት የሚመሰርቱበት ነው፡፡ ግጥም የሚያወርደው ወንድ ከሴቶች መሀል የመረጣትን ያሞግሳታል፡፡ ወይንም ይተቻታል ሴቷም እንዲሁ፡፡ እንዳልኩህ በእዚህ መሀል የከንፈር ወዳጅነትም ይመሰረታል፡፡ ከንፈር ሲሳሳሙ ደግሞ የሴቷ ከንፈር ምልክት እስኪያወጣ ድረስ መሳሳም የሚደረግበት ነው ሂቦንጎ፡፡
ዘሃበሻ፡-‹‹ሂቦንጎ›› የሚለው ዘፈንህ ከኢትዮጵያም አልፎ በውጭ ሀገር እየተደመጠልህ ነው፡፡ ስትሰራው ይህንን ጠብቀህ ነበር?
ስንታየሁ፡- በፍፁም አልጠበኩም፡፡ በእውነት ነው የምልህ የስራው ውጤት እንዲህ ይሆናል የሚል ግምት አልነበረኝም፡፡ ከጠበኩት በላይ ነው የሆነው፡፡ በጣም ብዙ ስልክ ነው አሁን የሚደወልልኝ፡፡ ከኢትዮጵያ የተለያዩ ክልሎ ች ሁሉ ይደወልልኛል፡፡ ከደቡብ አፍሪካ ሁሉ ይደወልልኝ ነበር፡፡ የዓለም ዋንጫ በደቡብ አፍሪካ ይካሄድ በነበረበት ወቅት ለስራ ብዙም አይወጡም ነበር፡፡ ‹‹አንድ ቤት ተሰብ ስበን ስራህን እየሰማን ነው›› ብለው የደወሉልኝ አሉ፡፡
ሃበሻ፡- ይህ ዘፈን አንተ በነፃ መስጠትህን አውቃለሁ፡፡ ተሸጧል የሚልም ነገር ሰምቻለሁ፡፡ ስለሽያጩ የምታውቀው ነገር አለ?
ስንታየሁ፡- እኔ አልሸጥኩም፡፡ በሀገራችን ላሉ የመገናኛ ብዙሃኖች ሰጠሁ፡፡ ከእዚህ ውጭ ሆሳዕና ለማውቃቸው ልጆች አንድ፣ ሁለት ሲዲ ሰጥቼ ነበር፡፡ የሚገርምህ ዘፈኑ በሶስት ቀን ውስጥ ነው የሆሳዕና ከተማን ያዳረሰው፡፡ በቅጂ ነው ከተማው የተዳረሰው፡፡ በስፋት የደረሰው በእዚህ ምክንያት ነው እንጂ እኔ አልሸጥኩም፡፡
ዘሃበሻ፡- ግን ደውሎ ያንተን ስራ እንደገዛ የነገረህ ሰው የለም?
ስንታየሁ፡- ገዛን የሚሉ ሰዎች ከሆሳዕናም ሆነ ከተለያዩ አካባቢዎች ይደውሉልኛል፡፡ ‹‹በሃምሳ ብር፣ በመቶ ብር ዛሬ ሲዲህን ገዛን ብለው ደውለው የነገሩኝ ሰዎች አሉ፡፡››
ዘሃበሻ፡- አንተ በነፃ የሰጠኸውን ሌሎች ሸጠው በገንዘቡ ተጠቃሚ በመሆናቸው ምን ይሰማሃል?
ስንታየሁ፡- በጣም ነው እኔ የምቆጨው፡፡ የለፋነው እኛ ነን፡፡ ስራውን በእዛ መልክ ለሙያው አፍቃሪ ለማድረስ ተጨንቀናል፡፡ እንዲህ ሆነን የሰራነውን ስራ ሌሎች እየሸጡ ሲጠቀሙበት እንዴት አይቆጭም? የሰራው እኮ ምንም አልተጠቀመበትም፡፡ የተጠቀመበት ሌላው ነው፡፡ ይህ መሆኑ በጣም ነው የሚቆጨው፡፡
ዘሃበሻ፡- በዘፈንህ ክሊፕ ላይ የውጭ ሀገር ዜጎች አሉ፡፡ እነሱን ማካተቱ ለምን አስፈለገ?
ስንታየሁ፡- ክሊፑ ላይ እንደተመለከትከው ካርታ አሳያቸዋለሁ፡፡ ሃዲያ ውስጥ ያሉ ሲታዩ የሚገባቸውን የቱሪስት መስህቦችን ማለት ነው፡፡ ያንን ለማሳየት ነው የፈረንጆቹን ለመጠቀም የቻልነው፡፡
ዘሃበሻ፡- እነዚህ የውጭ ሀገር ዜጎች በአጋጣሚ በቀረፃ ወቅት የተገኙ ናቸው ወይንስ ታስቦበት ነው እንዲገቡ የተደረገው?
ስንታየሁ፡- ታስቦበት ነው የሆነው፡፡ ካርታውን ለጎብኚዎች እያሳየን የቱሪዝም መስህቦችን የመጠቀም ሀሳቡ ሲመጣልን በእኛው ልጆች ነበር ለመስራት ያሰብነው፡፡ በኋላ ግን ለምን የውጭ ሀገር ሰዎች አይሆኑም የሚል ሀሳብ መጣና ፈረንጆቹን አስገባን፡፡
ዘሃበሻ፡- የ‹‹ሂቦንጎ›› ዘፈን መወደድ፣ ከጠበከው በላይ በሙያው አፍቃሪ ዘንድ ተቀባይነት ማግኘት ስንታየሁን ለቀጣይ ስራው ምን ያህል አነሳስቶታል?
ስንታየሁ፡- በጣም ነው ለስራ ያነሳሳኝ፡፡ እኔ አዲስ አበባ ተወልጄ ያደኩት ሆሳዕና ነው፡፡ ቋንቋውን እችላለሁ፡፡ የሚገርምህ እንደ ሂቦንጎ ያልወጡ ጥሩ ጥሩ የባህል ዘፈኖች አሉ፡፡ እነዚህን በጥሩ ሁኔታ አቀናብሮ ወደ አድማጭ ለመስራት በጣም ተነሳስቻለሁ፡፡ ቀደም ሲል እንደነገርኩህ ሂቦንጎ የሚለው ዘፈን ይህንን ያህል ተቀባይነት ያገኛል ብዬ አልጠበኩም ነበር፡፡ የሂቦንጎን ውጤት ላይ ግን የበለጠ እንድሰራ አድርጎኛል፡፡ በቅርቡም አዲስ የሚወጣ ስራ አለኝ፡፡ ‹‹ሸምበላላ›› የሚል ነው ርዕሱ፡፡ በሃዲያኛ ‹‹ሸምበላላ›› ማለት ‹‹ብዙ›› እንደማለት ነው፡፡ የሙዚቃ ክሊፕ ላይ እንዳየኸው ከብቶቹ ላይ ማርና ወተት ነው የሚረጨው፡፡ የሃዲያ አርቢዎች ከብቶቻቸው በቁጥር መቶ ሲሞሉ፣ አንድ ሺህ ሲሞሉ ያስቆጥራሉ፡፡
ዘሃበሻ፡- የከብቶቹ ቁጥር ከመቶ በታች ከሆነ አይቆጠርም?
ስንታየሁ፡- አዎ! መቶ ሲደርስ ነው የሚቆጠረው፡፡ ‹‹ጢቤ ወገንማ›› ነው የሚባለው ሂቦንጎ… ወደ ገጽ 16 የዞረ
ስርዓቱ፡፡ ከብቶችህ መቶ ሲሞሉ ታስቆጥራለህ፡፡ ስታስቆጥር ግን የከሱ ከብቶችና በቅርብ የተወለዱ ጥጃዎች በቆጠራው አይካተቱም፡፡ ደህና ደህና ከብቶች ናቸው የሚቆጠሩት፡፡ በዛ ላይ ‹‹ሸምበላላ›› ይባላል፡፡ ከብቶቹ ብዙ ናቸው እንደማለት ነው፡፡ በዚህ ፕሮግራም የሚዘፈን ዘፈን ነው የሰራሁት፡፡ ‹‹ሸምበላላ›› የሚባል ማለት ነው፡፡ ይህ ዘፈን በቅርብ ይወጣል፡፡
ዘሃበሻ፡- እዚህ አዲስ አበባ የምሽት ክበብ፣ መድረኮች ትሰራለህ?
ስንታየሁ፡- አዎ! እሰራለሁ፡፡ ሠርጎችን፣ የመድረክ ዝግጅቶችንም እሰራለሁ፡፡ በሀበሻ ሬስቶራንትም የምሽት ክበብ እየሰራሁ ነው ያለሁት፡፡
ዘሃበሻ፡- በልጅነትህ ሆሳዕና እያለህ እረኝነት ሞክረሃል?
ስንታየሁ፡- እረኝነት ወጥቻለሁ፡፡ እርሻም አርስ ነበር፡፡ እንጨት እሰብር ነበር፡፡ አጥርም አጥር ነበር፡፡ ያደኩት ገጠር አካባቢ ስለሆነ የገጠር ልጆች የሚሰሩትን ሁሉ ሞክሬያለሁ፡፡
ዘሃበሻ፡- በአያት እጅ ሆሳዕና እንዳደክ ነግረኸኛል፡፡ በአያት እጅ ያደገ ደግሞ ሞልቃቀ ነው የሚባል ነገር አለ፡፡ ስንታየሁ ሞልቃቃ ሆኖ ነው ያደገው?
ስንታየሁ፡- እኔ አይደለሁም፡፡ የሚገርምህ አያቴ ያሞላቅቀኛል፡፡ ግን መቅጣት ካለበት ደግሞ ይቀጣኛል፡፡ በጣም ሀይለኛ ነው፡፡ ያሞላቀቅቀኛል ደግመም ይቀጣኝ ነበር፡፡ በጣም ነው ደግሞ የሚወደኝ፡፡ የሚገርምህ ትንሽ ልጅ ሆኜ አንድ ቀን አንድ ነገር አጥፍቼ ይቀጣኝ ነበር፡፡ እሱ ሲገርፈኝ ጎረቤት አካባቢ የነበረች ሴትዮ ‹‹ቅጣው ይሄ ባለጌ›› እያለች ታያለች፡፡ አያቴ እኔን ገርፎኝ ንዴቱ ከበረደለት በኋላ ቀጥታ ሄዶ ከሴትየዋ ጋር ነው መጣላት የጀመረው፡፡
ዘሃበሻ፡- ለምን?
ስንታየሁ፡- እኔ ተናድጄ ነው፡፡ ልጄን ስገድለው ለምን አትገላግይኝም ብሎ ነው የተጣላው፡፡ እንዳልኩህ አያቴ ቢያሞላቅቀኝም በስርዓቱ እንዳድግ ይቀጣኝ ይመክረኝም ነበር፡፡
ዘሃበሻ፡- ለመዝፈንም የሚያበቃኝ ድምፅ ስላለኝ ወደ ሙያው መግባት አለብኝ ብለህ የወሰንክበትን ጊዜ ታስታውሰዋለህ?
ስንታየሁ፡- እንዳልኩህ ሆሳዕና ከተማ ውስጥ ክበባት የለም፡፡ ችሎታህን የምታወጣበት ነገር የለም፡፡ እኔ ግን ቤት ውስጥ እዘፍን ነበር፡፡ እኔ ቤት ውስጥ ከሆንኩኝ ቴፑ በጭራሽ ዝም አይልም፡፡ የሚገርምህ ከማብዛቴ የተነሳ እናቴ የቴፑን ሶኬት ደብቃብኝ ሁሉ ትሄድ ነበር፡፡ በጣም ነበር የምዘፍነው፡፡ ከቤት ውጭም እዘፍን ነበር፡፡ ድምፄን የሰሙ ሰዎች ‹‹ለምን ዘፋኝ አትሆንም?›› ሲሉኝ ለካ መዝፈን እችላለሁ አልኩኝ፡፡ የወንድ የለ፣ የሴት የለ የሁሉንም ዘፋኞች ዘፈን ማጥናትና መዝፈን፣ እንዲሁም ራሴ መሞከር ጀመርኩኝ፡፡ በኋላ እዚህ አክስቴ ስለነበረች በቀጥታ እሷ ጋር ነው የመጣሁት፡፡ ወ.ወ.ወ.ክ ስልጠናውን ወሰድኩ፡፡ የሚገርምህ ‹‹ሪትም›› ምን ማለት እንደሆነ አላውቅም፡፡ ግን ስዘፍን ከሪትም ወጥቼ አላውቅም ስዘፍን ‹‹ሜዠርህ›› ምን ላይ ነው? ተብዬ ስጠየቅ ሙዚቃውን አውቀዋለሁ ነበር የምለው፡፡ ‹‹ሜዠር›› ምን ማለት እንደሆነ አላውቅማ! ግን ሙዚቃውን ሲሰሩልኝ ከቅኝት ላልወጣ ነበር የምዘፍነው፡፡ አሁን ሳስታውሰው ለራሴ ይገርመኛል፡፡
ዘሃበሻ፡- ስለዘፈንክ ተብሎ ለመጀመሪያ ጊዜ ምን ያህል ተከፈለህ?
ስንታየሁ፡- በክበብ ውስጥ እያለን የመድረክ ዝግጅት ስንሰራ አስር ወይንም ሃያ ብር ነበር የሚሰጠን፡፡ ከዚያ በኋላ ሠርግ ሰርቼ ሠላሳ ብር ተከፍሎኛል፡፡
ዘሃበሻ፡- ትልቅ ገንዘብ ነበር?
ስንታየሁ፡- አዎ! እናቴ ገንዘብ ትልክልኝ ነበር፡፡ ግን እናቴ ከምትልክልኝ ገንዘብ ይልቅ ሠርግ ሰርቼ ያገኘኋት ሠላሳ ብር ለእኔ ትልቅ ነበረች፡፡
ዘሃበሻ፡- ስንታየሁ የሙሉ አልበም ስራህስ?
ስንታየሁ፡- ቀደም ሲል እንደነገርኩህ ሁለተኛውን ነጠላ ዜማዬን ጨርሻለሁ፡፡ ከዚህ በኋላ ወደ ሙሉ አልበም ስራዬ ነው የምሄደው፡፡
ዘሃበሻ፡- እስካሁን በኪነ-ጥበብ መንገድ የተጓዝክበት መንገድ አልጋ ባልጋ ነበር?
ስንታየሁ፡- ብዙ ፈታኝ ነገር ነበረበት፡፡ ጉዞው ቀላል አይደለም፡፡ የምሽት ክበብ ስጀምር የጀመርኩት ዲ-አፍሪክ ሆቴል ነበር፡፡ በሳምንት ሁለት ቀን ነበር የምንሰራው፡፡ ድሮ ስጀምርና አሁን ያለኝ ድምፅ ይለያያል፡፡ አሁን የተሻለ ድምፅ ነው ያለኝ፡፡ ድምፄ የተሻለ እንዲሆን መልፋት ያስፈልገኝ ነበር፡፡ አዲስ ከተማ ወወክማ ስንሰራ ለልምምድ የምንገናኘው ስምንት ሰዓት ነበር፡፡ እኔ ግን ሰባት ሰዓት ተገኝቼ የድምፅ ልምምድ እሰራ ነበር፡፡ ለአንድ ድምፃዊ የድምፅ ልምምድ መስራት የግድ አስፈላጊ ነገር ነው፡፡ እንዳልኩህ በብዙ ልፋት ነው አሁን የደረስኩበት ደረጃ የደረስኩት፡፡ የምሽት ክበብ ስትሄድ አንዱ ጋ‹‹ጥሩ ድምፅ አለህ›› ሊሉህ ይችላሉ፡፡ አንዱጋ ደግሞ ‹‹ዘፋኝ ነኝ ብለህ ነው?›› ሊሉ ይችላሉ፡፡ እኔ ግን እንደ እሱ አይነት ነገር አላጋጠመኝም፡፡ ግን ልፋት አለው፡፡ ድካም አለው፡፡
ዘሃበሻ፡- ‹‹ሂቦንጎ›› ሙዚቃውንም ክሊፑንም ለመስራት ያወጣችውን ወጭ መልሰሃል?
ስንታየሁ፡- አልመለስኩም፡፡ የክልሉ መንግስት ግን የተወሰነ ግማሽ ብር ሸፍኖልኛል፡፡ ክሊፑ ላይ የለበስኩት ልብስ ደግሞ ውድ ነበር፡፡ መግዛት አልችልም፡፡ እሱንም የሆሳዕና የካቢኔ አባላት ናቸው አውልቀው የሰጡኝ፡፡ በእዚህ አጋጣሚ እነሱንም አመሰግናቸዋለሁ፡፡
ዘሃበሻ፡- እኔ ግን በ‹‹ሂቦንጎ›› ዘፈን መሬት ተሰጥቶታል የሚባል ነገር ሰምቻለሁ?
ስንታየሁ፡- አንተ መሬት ብቻ ነው የሰማኸው?
ዘሃበሻ፡- አዎ! ሌላም አለ?
ስንታየሁ፡- የሚባለው ነገርማ ብዙ ነው፡፡
ዘሃበሻ፡- ምን ምን ይባላል?
ስንታየሁ፡- እንዳልከው መሬት አግኝቷል ይባላል፡፡ ብዙ ብር በሽልማት አግኝቷል ይባላል፡፡ ኧረ ብዙ ነገር ነው የሚባለው፡፡ የሚባለውን ሁሉ ግን እኔ አላገኘሁም፡፡ ከሁሉ በላይ ደስ የሚለኝ ያደኩበትን አካባቢ ባህላዊ ዘፈን በእዚህ መልክ ለሙያው አፈቃሪ ማስተዋወቅ በመቻሌ ነው፡፡ መጀመሪያ የመሬት ሽልማቱን አስቤ አልሰራሁም፡፡ ቀደም ሲል እንዳልኩህም ዘፈኑ እንዲህ ይወደዳል ብዬም አልገመትኩም፡፡ በእርግጥ የሀዲያ ባህሉ፣ ታሪክ ብዙም አልወጣም፡፡ ግን ብዙ ሊያሰሩ የሚችሉ፣ ሊወጡ የሚገባቸው ነገሮች አሉ፡፡ ካልተሰራው ብዙ ነገር እጅግ በጣም ጥቂቱን ለማውጣት ብዬ እንጂ የመሬት ሽልማትን አስቤ አልሰራሁም፡፡
ዘሃበሻ፡- መስከረም 13 እና 14 ሀዲያ ላይ የሚዘጋጅ አንድ ሲምፖዚየም አለ፡፡ እዚህ ላይ ትገኛለህ ብዬ አስባለሁ፡፡
ስንታየሁ፡- በእርግጥ እገኛለሁ፡፡ አዲሱ ነጠላ ዜማዬንም የሰራሁት ለእዛ ነው፡፡ ሰው ለበለጠ ስራ እንዲነሳሳ የሚያደርግም ስራ ነው፡፡ በሲምፖዚየም ላይ በትክክል እገኛለሁ፡፡
ዘሃበሻ፡- ክብደትህ ምን ያህል ነው?
ስንታየሁ፡- መጀመሪያ አንተ ገምት…
ዘሃበሻ፡- ከሰማኒያ እስከ ሰማኒያ አምስት ኪሎ ትሆናለህ ብዬ እገምታለሁ፡፡
ስንታየሁ፡- ክብደቴ አንድ መቶ ሶስት ኪሎ ግራም ነው፡፡
ዘሃበሻ፡- ከባድ አይደል?
ስንታየሁ፡- ቁመቴ ረጅም ነው፡፡ አንተ ገምት ስልህ እስከ ሰማኒያ አምስት ኪሎ ብለህ ነው የገመትከው፡፡ በእርግጥ በወተት ስላደኩ ከልጅነት የመጣ ክብደት ነው፡፡ እንደምታየው ቦርጭ የለኝም፡፡ ስፖርት እሰራለሁ፡፡ ስፖርት መስራት እወዳለሁ፡፡ ከሙያው ውጭ የእረፍት ጊዜዬን የማሳልፈው በማንበብና ስፖርት በመስራት ነው፡፡ ከቁጥር አንድ ጀምሮ የእናንተ መጽሔት አለኝ፡፡ ከፋይል የጠፋብህ ካለ ላውስህ እችላለሁ፡፡ ሌሎችም እንዲሁ አሉ፡፡ ከማንበብ በተጨማሪ የዋና ስፖርት እወዳለሁ፡፡ ጂም እሰራለሁ፡፡
ዘሃበሻ፡- ውፍረት ለጤና ጥሩ አይደለም የሚሉ ሰዎች አሉ፡፡ ውፍረት የሟቾች ምልክት ነው የሚሉ ሰዎችም አሉ፡፡ በአንተ እምነት የየትኛው ሀሳብ ነው ልክ?
ስንታየሁ፡- እኔ ውፍረት የምቾት ምልክት ነው አልልም፡፡ ለጤናም ለእንቅስቃሴም ቀልጠፍ ሲባል ነው ደስ የሚለው፡፡ እኔ ስፖርት ስለምሰራ እንደ ክብደቴ አይደለሁም፡፡ ቀልጠፍ ብዬ ነው የምሰራው፡፡
ዘሃበሻ፡- በነገራችን ላይ ‹‹ሂቦንጎ›› የሚለው ዘፈንህ ሀዲያ ውስጥ በመድረክ ለተመልካች አቅርበህ ታውቃለህ? ወይንስ በክሊፑ ብቻ ነው የሚያውቅህ?
ስንታየሁ፡- ዝግጅት ተዘጋጅቶ አንድ ሁለት መድረክ ሰርቻለሁ፡፡ ብዙ ህዝብ የሚሰበስብበት ዝግጅት ነበር፡፡ በእዚህ ዝግጅት ላይ ነው ሆሳዕና ውስጥ የሰራሁት፡፡
ዘሃበሻ፡- እኔ ጥያቄዬን እየጨረስኩ ነው መታለፍ የለበትም የምትለው ነገር አለ?
ስንታየሁ፡- የሚፈቀድልኝ ከሆነ ማመስገን የምፈልጋቸው ሰዎች አሉ፡፡
ዘሃበሻ፡- እድሉን ሰጥቼሃለሁ ቀጥል…
ስንታየሁ፡- አሁን በህይወት የሌለችው ያሳደገችኝ እናቴን ኑራሜ ሎሚሳኮን፣ እንዲሁም እናቴን ቦጋለች ጥላሁንን፣ ወይንሸት ገለታን በጣም ነው የማመሰግናቸው፡፡ ሶስቱም የምወዳቸውና የሚወዱኝ ናቸው፡፡ እንደወለዱኝ ነው የምቆጥረው፡፡ እነሱን በጣም አመሰግናለሁ፡፡ ሁሉንም አድምጠው በስልክና በአካል አስተያየት የሰጠኝንና መላውን የኢትዮጵያ ህዝብንም በጣም አመሰግናለሁ፡፡
ዘሃበሻ፡- እኔም ለነበረን ቆይታ አመሰግናለሁ፡፡ እግዚአብሔር ይስጥልኝ፡፡

↧
↧

ከአምቦ ተፈናቅለው በአንድነት ፓርቲ ጽ/ቤት የተጠለሉ የአማራ ተወላጆችን አስመልክቶ በፍኖተ ነፃነት ጋዜጣ ዝግጅት ክፍል የተቀነባበረ ዘጋቢ ፊልም

$
0
0
↧

እውነተኛው አ.ኢ.ግ.ተ. (EITI) ወይስ የማዳም ክላሬ የሙስና ማጋበሻ ቡድን? (ፕሮፌሰር አለማየሁ ገብረማርያም)

$
0
0

ከፕሮፌሰር አለማየሁ ገብረማርያም
ትርጉም በነጻነት ለሀገሬ

ማዳም ክላሬ አሸንፈዋል! እንኳን ደስ ያለዎት፣ ማዳም ክላሬ!

ባለፈው ሳምንት የ “አምራች ኢንዱስትሪዎች የግልጽነት ተነሳሽነት/Extractive Industries Transparency Initiative (EITI) ሊቀ መንበር የሆኑት ማዳም ክላሬ ሾርት ስልጣናቸውን ከህግ አግባብ ውጭ በመጠቀም እና በማስፈራራት በኢትዮጵያ ያለው ገዥ አካል የሙስና ማጋበሻ ቡድናቸው አባል እንዲሆን ለማስቻል የEITI የቦርድ አባላት ድምጻቸውን እንዲሰጡ በማድረጉ ጥረት ሲያካሂዱት የቆዩት ዥዋዥዌ ጨዋታ ተሳክቶላቸዋል፡፡ ማዳሟ አሮጌውን እና ያረጀ ያፈጀውን የአሰራር ሂደትን ማለትም እጅ በመጠምዘዝ፣ በኃይል በማስፈራራት፣ ስልጣንን ከህግ አግባብ ውጭ በመጠቀም በማስገደድ፣ ከኋላ ሆኖ በማስተኮስ፣ ስልጣንን መከታ በማድረግ ከህግ አግባብ ውጭ በግድ እንዲያምኑ በማድረግ፣ አሰልች እና የምጸት ቃላትን በመጠቀም እና የህጻናት ዓይነት እሽሩሩ ዘይቤ ቁጣን በመከተል ለርካሽ ጥቅም ሲባል የሞት ሽረት ትግል በማድረግ ሀቅን በመደፍጠጥ በሸፍጥ ለጊዜውም ቢሆን ሀሳባቸውን አሳክተዋል፡፡ ማዳሟ በእንደዚህ ዓይነት እኩይ ምግባራቸው የተካኑ ናቸው፡፡ እ.ኤ.አ በ2003 እንግሊዝ እና አሜሪካ በኢራቅ ላይ ወረራ ለማካሄድ በተዘጋጁበት ጊዜ ማዳም ሾርት በቶኒ ብሌር ላይ ጠንካራ የሆነ ትችት በማቅረብ ከመንግስታቸው ዓለም አቀፍ የልማት ጸሐፊነት ስልጣናቸውን በገዛ ፈቃዳቸው እንደሚለቁ በማስፈራራት ሁኔታውን በመቃወም የኃይል ትችት አቅርበው ነበር::   ብሌርንና የአሜሪካን መንግስት ሲተቹ አንዳሉት “ሆኖም ግን በዚያም ተባለ በዚህ የጦርነቱ መካሄድ አይቀሬነት በተረጋገጠበት ወቅት፣ ሌሎችን አገሮች በኃይል እና በማስፈራራት ለጦርነቱ መካሄድ ድጋፍ እንዲሰጡ ያስገድዱ ነበር፡፡“EITI board chairwoman

አንደ ኢራቁም ጉዳይ: ማዳም ክላሬ “በኢትዮጵያ ያለው ገዥ አካል ድምጽ በማግኘት የEITI አባል እንዲሆን ከህግ አግባብ ውጭ ስልጣንዎን በመጠቀም  የቦርድ አባላትዎን ያስገድዱ እና ያሳምኑ እንደነበር እናውቃለን፡፡“ እንኳን ደስ ያለዎት! ድል ተቀዳጅተዋል፡፡ የድል ደረጃ አድርገው ይውሰዱት፣ ጣራውን ከፍ ያድርጉት፡፡ “ለሰብአዊ መብት የሚሟገቱትን ድል አድርገዋል፣ በእራስዎ ቦርድ ያሉትን የሲቪል ማህበረሰብ ተወካዮችን በመላው ዓለም ፊት አዋርደዋል፣ እናም ዕድለቢሶችን እና ድምጽ አልባ የኢትዮጵያ ዲያስፖራ ማህበረሰብ አባላትን አባርረዋል፣ “መብቶቻቸውንም” ደፍጥጠዋል፣ አሁን አዲስ አበባ በመሄድ የስኬት በዓልዎን ቸበርቻቻ ማክበር ነው፡፡ በትግል ያገኙት ውጤት ነውና፡፡ ቻምፓኝ እና ኮኛክ እንደ ጅረት ውኃ ይፍሰስ፡፡ አሁን EITIን የእርስዎ የግል ንብረት አድርገውታል፡፡ የእራስዎ ህጻን ነው! ለ EITI አዲስ ስም ያውጡለት፡፡ የማዳም ክላሬ የሙስና ማጋበሻ ድርጅት በሉት? ጥሩ የእምነተቢሶች የመጠሪያ ስምን ይዟል፡፡

በጣም የሚያስደንቀው እውነታ ግን የማዳም ሾርት ፍልስፍና (እራሳቸው “መርህ” እያሉ የሚጠሩት) በብዙ በሙስና በተዘፈቁ አገሮች የማዕድን እና አምራች ኢንዱስትሪዎች ዘርፍ ላይ ዕዉን እየሆነ መጥቷል፡፡ በኢትዮጵያ ያለውን ገዥ አካል የEITI አባል በማድረጉ እረገድ ማዳም ሾርት የማዕድን ሙስናን ለመቆጣጠር የሚያስችል ቀላል እና በሚከተለው ዳህራ ላይ ትኩረት ያደረገ በአጭር ርቀት ላይ የተመሰረተ ድሁር ህልዮት ቀምረዋል፤ ህልዮቱም እንዲህ ይላል፣ “በዓለም ላይ በጣም በሙስና የተዘፈቁ ገዥ አካላት የይስሙላ የግልጽነት እና ተጠያቂነት ካባን ደርበው የEITI አባል እንዲሆኑ መፍቀድ፡፡“ ከዚያም እግሮችን በማንሸራተት መደነስ እና ማቀንቀን፡፡ ስለግልጽነት እና መልካም አስተዳደር ጥቂት አስመሳይ ቃላትን እና ሀረጎችን በማነብነብ የህዝብ እምነትን ለማግኘት የማታለያ ጥረት ማድረግ፡፡ የውሸት በእመኑኝ ላይ የተመሰረቱ ጥሩ የሚመስሉ የቢሮክራሲ ፍሬ ከርስኪ የታጨቁበት የማመልከቻ ቅጽ መሙላት፡፡ ከዚያም በማዕድን ዘርፍ ስራው ጥሩ ተሞክሮ እና ታማኝ መሆናቸውን በመግለጽ የአባልነት ጥያቄውን የምስክር ወረቀት ለማግኘት መጠየቅ፡፡ በመጨረሻም ከደስታ የመጨረሻው ከፍተኛ እርከን ላይ በመድረስ ሰርግ እና ምላሽ ማድረግ ትልቁ ግባቸው ነው፡፡ በሌላ አገላለጽ ማዳም ክላሬ ሾርት ገዥውን አካል የጸረ ሙስና ተዋጊ ጦር አስመስሎ በማቅረብ እንዲሁም ወሮበላ ዘራፊዎችን እና ሸፍጠኛ ወንጀለኞችን በእራሳቸው ተለክቶ የተሰፋ የማስመሰያ ካባ በማልበስ በዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ፊት የተከበሩ የአገር መሪዎች አስመስሎ ለማሳየት እና ለቀጣዮቹ ሶስት ዓመታት ያለምንም እንከን የጥሩዎች ሁሉ ተምሳሌት አድርጎ ለማቅረብ የተቀመረ ስሌት ነው፡፡ እንግዲህ በዚህ መንገድ ነው በአፍሪካ እና በሌሎች አገሮች ያለው በሙስና የበከተው የማዕድን እና የተፈጥሮ ጋዝ ዘርፍ በማዳም ክላሬ ሾርት ከሙስና የማጽዳት የአሰራር ዘይቤ የተቃኘው፡፡

በኢትዮጵያ ያለው ገዥ አካል የEITI አባል እንዲሆን የተሰጠው ውሳኔ ፍጹም በሆነ ሙስና የተደረገ እና የማስመሰያ የአባልነት ተውኔት ነው፡፡ እ.ኤ.አ በ2010 ገዥው አካል ለአባልነት ያቀረበው ጥያቄ ውድቅ በተደረገበት ጊዜ የተሰጠው ምክንያት:- “የኢትዮጵያ የበጎ አድራጎት እና ማህበራት አዋጅ’ የሲቪል ማህበረሰብ ቡድኖች በነጻነት እንዳይንቀሳቀሱ በሂደትም ትርጉም ያለው ተሳትፎ እንዳያደርጉ ደንቃራ ሆኗል ወደፊትም ይሆናል፤ ስለሆነም ‘የበጎአድራጎትእናማህበራትአዋጅ’ እስካልተወገደድረስኢትዮጵያየEITIአባልእንድትሆንእንደማይወስን በተጨባጭ ገልጾ ነበር፡፡ በ EITI ታሪክ በእንደዚህ ያለ የአፋኝነት ህግ መሰረት ከሰብአዊ መብት አጠባበቅ ጋር በተያያዘ መልኩ አንዲት አገር የድርጅቱ አባል እንዳትሆን የአባልነት ጥያቄው ውድቅ ሲደረግ የመጀመሪያው እና ብቸኛው ክስተት ነው፡፡ (የተሰመረው አጽንኦ ለመስጠት ነው)፡፡

ታዲያ ኢትዮጵያን በአሁኑ ጊዜ በአባልነት ለመቀበል የተቻለው በስራ ላይ እየተተገበረ ያለው “የበጎ አድራጎት እና ማህበራት አዋጅ” ተለውጦ ነው? እ.ኤ.ኤ ከ2010 ጀምሮ በኢትዮጵያ የሲቪል ማህበረሰብ እንቅስቃሴ ላይ ምን የተለወጠ ነገር አለ? “በአዋጁ” መውጣት እና በስራ ላይ መዋል ቀጥተኛ እንደምታ ምክንያት እ.ኤ.አ በ2010 ብዛታቸው 4,600 የነበሩት የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች በአስደንጋጭ ሁኔታ ቁጥራቸው አሽቆልቁሎ በሶስት ወራት ጊዜ ውስጥ በዓመቱ መጀመሪያ አካባቢ 1,400 ሊሆኑ  ችለዋል፡፡ “ከእነዚሁ ከተረፉት እና በሞት የሽረት ትግል ውስጥ በመንፈራገጥ ላይ ከሚገኙት ድርጅቶች ውስጥ ደግሞ በአዋጁ አሳሪነት ምክንያት 90 በመቶ ወይም ከዚያ በላይ የሚሆነውን የሰው ኃይላቸውን እንዲቀንሱ ተገደዋል፡፡”

በሶስት ወራት ውስጥ በአንድ ጊዜ እርምጃ ብቻ “አዋጁ” በኢትዮጵያ 70 በመቶ የሚሆኑትን የሲቪል ማህበራት ድርጅቶችን ከስራ ውጭ አድርጓቸዋል፡፡ እ.ኤ.አ በፌብሯሪ 2010 ገዥው አካል ከተመሰረተ ብዙ ጊዚያትን ያስቆጠረውን የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ጉባኤን እና የኢትዮጵያ የህግ ባለሙያ ሴቶች ማህበርን በተጨባጭ የእነዚህን ሁለት ጠንካራ ተቋማት አቅም ሽባ ለማድረግ፣ እንዲሁም ደግሞ ሊያሳኩ የሚያስቧቸውን የተቋቋሙባቸውን ዝንባሌዎች እና ዓላማዎች ከህግ አግባብ ውጭ በሆነ መልኩ ለማስተጓጎል በማሰብ ሀብታቸውን እንዳያንቀሳቅሱ አገደ፡፡

የEITI የቦርድ አባላት እ.ኤ.ኤ በ2010 የገዥውን አካል የአባልነት ጥያቄ ውድቅ ካደረገ በኋላ በእርግጠኝነት አንድ ነገር ተለውጧል፡፡ እ.ኤ.አ በማርች 2011 ማዳም ክላሬ ሾርት የEITI የቦርድ ሊቀ መንበር ሆነው ተመርጠዋል፡፡ ማዳም ሾርት ለብዙ ጊዜ ተደናቂ መሪ እና በኢትዮጵያ ላለው ገዥ አካል ሻምፒዮን እንዲሁም በቅርቡ የአረፉት የአቶ መለስ ዜናዊ  ከፍተኛ አድናቂ ናቸው፡፡ በአቶ መለስ ዜናዊ ላይ ያመልካሉ፡፡ የሚያመልኳቸው ግን በጥሩ ነገር ተምሳሌትነታቸው አይደለም፡፡ ምናልባትም እ.ኤ.አ በ2010 ገዥው አካል የድርጅቱ አባል እንዳይሆን ውድቅ ያደረጉትን የEITI የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ተወካዮች እና የስራ ባልደረቦቻቸውን ክብር እና ሀሳብ ለማንኳሰስ እንዲሁም በወሰንየለሽ አፍቅሮ የተዘፈቁበትን ገዥ አካል ሽንፈት ለመበቀል ያደረጉት ሊሆን ይችላል ተብሎ ይገመታል፡፡ ከሁሉም በላይ ደግሞ የገዥው አካል የአባልነት ጥያቄ ውድቅ በተደረገበት ጊዜ በ EITI ታሪክ በእንደዚህ ያለ የአፋኝነት ህግ መሰረት “በግልጽ ከሰብአዊ መብት አጠባበቅ” ጋር በተያያዘ መልኩ አንዲት አገር የድርጅቱ አባል እንዳትሆን ውድቅ ሲደረግ የመጀመሪያው እና ብቸኛው ክስተት  ስለነበረም ነው፡፡ ማዳም ሾርት በአቶ መለስ ዜናዊ እና ኩባንያቸው ላይ የደረሰውን “ውርደት” ለመበቀል ዕቅድ በማውጣት በዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ፊት የአቶ መለስን የመጀመሪያ የአባልነት ጥያቄ ውድቅ በማደረግ ቁልፍ ሚና የተጫወቱትን የEITI የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ተወካዮችን ማዋረድ ላይ ያጠነጠነ ነበር፡፡ ማዳም ክላሬ፣ በቀልተኛዋ አሁን የበቀል እርምጃዎን ወስደዋል፡፡!

ማዳም ክላሬ በኢትዮጵያ ላለው ገዥ አካል በመወገን እ.ኤ.አ ማርች 11/2014 ግልጽ ደብዳቤ በመጻፍ ድፍረት የተሞላበትን የዘመቻ ውትወታ (በማስገደድ አላልኩም) ሲጀምሩ በEITI በቦርድ አባልነት ባሉት የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ተወካዮች እንደ አላዋቂ ልጅ አጥፊዎች ያህል አውርደው በመመልከት የቁጣ ድምጻቸውን ከፍ በማድረግ አምባርቀውባቸዋል፡፡ እብደትን የተላበሰ የሚያስገርም ምልከታም አድርገዋል፡፡ እንዲህ የሚል ምልከታ፣ “የEITI መርሆዎችን የሚተገብሩ አገሮችን ሁኔታ በመምለከትበት ጊዜ በኢትዮጵያ ያለው የሲቪል ማህበረሰብ ድርጀቶች ሁኔታ በሌሎች አገሮች ከሚታየው በብዙ መልኩ የከፋ ነው የሚለውን አባባል አልቀበለውም፣“ በማለት ለእራስ ታላቅ ክብርን የሰጠ የድንፋታ ንግግር አሰምተዋል፡፡ ማዳሟ ይህንን ንግግር ሲያደርጉ ምን ለማለት ፈልገው ነው? ለመሆኑ የEITI አባላት እነማን ናቸው?

EITI በአሁኑ ጊዜ 40 ወይም ከዚያ በላይ የሚሆኑ አባል አገሮች አሉት፡፡ ብዙዎቹ አባል አገሮችም በዓለም ላይ በሙስና በበከቱ እና ጨቋኝ መንግስታት መዳፍ ስር እግር ከወርች ተተብትበው የሚገኙ ናቸው፡፡ ከእነዚህም ውስጥ አፍጋኒስታን፣ ቡርኪናፋሶ፣ ካሜሩን፣ የመካከለኛው አፍሪካ ሬፑብሊክ፣ ቻድ፣ የኮንጎ ዴሞክራቲክ ሬፑብሊክ፣ ጊኒ፣ ካዛኪስታን፣ ላይቤሪያ፣ ማሊ፣ ማውሪታንያ፣ ሞዛምቢክ፣ ኒጀር፣ ናይጀሪያ፣ የኮንጎ ሬፑበሊክ፣ ሴኔጋል፣ ሴራሊዮን፣ ታዣኪስታን እና የመን ይገኙበታል፡፡ “የኢትዮጵያ ሁኔታ ከሌሎች የከፋ አይደለም” ከሚለው ማነጻጸሪያቸው አንጻር ማዳም ሾርት በእርግጠኝነት አንድ ሊካድ የማይችል ሀቅን ተናግረዋል፣ ይኸውም በኢትዮጵያ ያለው ገዥ አካል ከሌሎች በገፍ የሰብአዊ መብት ድፍጠጣ ከሚፈጽሙት የEITI አባል አምባገነን አገሮች የከፋ አይደለም፣ ወይም ደግሞ ከብዙዎቹ የተለየ አይደለም ብለዋል፡፡ ሁሉም በሙስና የበከቱ ናቸው፡፡ ሁሉም የሲቪል ማህበረሰብ ተቋማትን ህልውና ግብአተ መሬት የፈጸሙ ናቸው፡፡ እናም የመመንተፊያ የቆዳ ቦርሳዎችን ተሸክመው ክው ክው የሚሉ ዘራፊዎች እና ወሮበሎች ናቸው፡፡ ማዳሟ ለቦርድ አባላቱ፣ ለሰብአዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች እና ለኢትዮጵያውያን/ት የዲያስፖራ ማህበረሰብ አባላት ለማስተላለፍ የፈጉት ትክክለኛው መልዕክት ግልጽ ነበር፡፡ “ሁሉንም ጸጥ ለማድረግ” ነው፡፡ ከተሰጣችሁ ቁመት በላይ አትንጠራሩ፡፡ በሙስና የበከቱ ዘራፊዎችን ሊፒስቲክስ በመቀባት የተለመደውን የቢዝነስ ስራ እናስቀጥል፡፡ በዚህ መንገድ መጓዝ አንችልምን?

ባራክ ኦባማ እጩ ፕሬዚዳንታዊ ተመራጭ በነበሩበት ጊዜ ከተናገሩት ጋር እስማማለሁ፣ “አሳማን ለማቆንጀት ሊፒስቲክ (የከንፈር ቀለም) መቀባት ይቻላል፣ ሆኖም ግን አሁንም ያው አሳማ ነው፡፡ አንድን ትልቅ አሳ በወረቀት መጠቅለል ይቻላል፣ እናም ለውጥ ብለን ልንጠራው እንችላለን፣ ሆኖም ግን መጠንባቱን አያቆምም ፡፡“ EITI ለዘራፊዎች በልክ ዩኒፎርም አሰፍቶ ማስመሰያ በማልበስ “ግልጽነት” እና “ተጠያቂነት” ብሎ ሊጠራቸው ይችላል፣ ሆኖም ግን ያው አሁንም ዘራፊዎች ናቸው፡፡ ሙስናን በEITI አርማ መጠቅለል ይቻላል እናም ንጹህ ብሎ መጥራት ይቻላል፣ ሆኖም ግን እስከ አሁንም መጠንባቱን አያቆምም ፡፡ EITI የአፍሪካ ዘራፊ ገዥዎችን ንጹህ እና ጨዋ ለማስመሰል የሚቀባ ሊፒስቲክ ነው፡፡

አዲስ በሆነ መልኩ ማዳም ሾርት በእርግጠኝነት ትክክል ናቸው፡፡ ለተፈጠረው ስህተት ይቅርታ እጠይቃለሁ! ብዙዎቹ በEITI አባል የሆኑ የአፍሪካ አገሮች በተኩላ ዘራፊ ሙሰኛ ገዥ ቡድኖች የሚሽከረከሩ ናቸው፡፡ “ዘራፊነት የአፍሪካ አምባገነናዊነት ከፍተኛው ደረጃ” በሚል ርዕስ ባቀረብኩት ትችት ህልዮት ቀምሬ ነበር፡፡ ማዳም ሾርት በገንዘቡ በኩል ትክክል ናቸው፡፡ በኢትዮጵያ ያለውን ዘራፊ ገዥ አካል በEITI ካለው ከትክክለኛ ቦታው ታላቁ የሙስና ጠረጴዛ ላይ ለምን ነጠሉት? በእውነት ይህ ጉዳይ ፍትሀዊ አይደለም፡፡

የበለጠ ከዚህ በተለየ መልኩ ማዳም ሾርት የእኔን ነጥብ በትክክል አረጋግጠውታል፡፡ በእርግጥ EITI ማዕከላዊ የማዕድን ሙስና ቡድን ነው፡፡ አሊባባን እና 40ዎቹን ሌቦች አስታወሰኝ፡፡

አሁንም በጣም በተለየ መልኩ ማዳም ሾርት በኢትዮጵያ ያለው ገዥ አካል የአባልነት ጥያቄው ተቀባይነት እንዲያገኝ እና በEITI ሲስተም እንዲገባ ለማድረግ በግልጽ ደብዳቢያቸው ላከናወኑት የሞት የሽረት ትግል በጣም ላመሰግናቸው እፈልጋለሁ፡፡ ከልብ በመነጨ መልክ ላደረጉት የትግል መንፈስ አደንቃቸዋለሁ፡፡ ማዳም ሾርት በእርሳቸው መንገድ የማይቆሙትን ማንንም ቢሆን የማዋረድ ስብእና ያላቸው ሰው ናቸው፡፡

የገዥውን አካል የአባልነት ጥያቄ ቦርዱ እንዲያጸድቀው በማስገደድ ማዳም ሾርት ታላቅ አገልግሎት አበርክተውልናል፡፡ ምንም በውል ሳያጤኑት EITI በእውን ምን ዓይነት ተቋም እንደሆነ እንዲሁም በህገወጥ መንገድ ጥቅም ለማግኘት የማስጠበቂያ የጫጫታ ቡድን መሆኑን አጋልጠዋል፡፡ በተደራጁ የወንጀለኞች ድርጅቶች የጥቅም ማስጠበቂያ የጫጫታ ቡድኖች የፖሊስ እና የፍትህ አካላቱ በትክክል ህዝቡን ማገልገል ሲሳናቸው ወይም ደግሞ ለማህበረሰቡ የህግ ጥበቃ ማቅረብ ሳይችሉ ሲቀሩ የሚከሰቱ ናቸው፡፡ “በጥቂት የክፍያ ገንዘብ” ሰበብ በሸፍጥ የተካነው ወንጀለኛ ለደንበኞቹ “ህግ እና ስርዓትን” ያስከብራል፣ እናም በሌሎች ወሮበሎች እና አዲስ ወንጀለኞች እንዳይዘረፉ ጥበቃውን ሊያረጋግጥ ይችላል፡፡

አብዛኞቹ የEITI አባል አገሮች በራሳቸው የህግ ተቋማት ሙስናን የመቆጣጠር አቅሙ የላቸውም፡፡ ብዙዎቹ አባል አገሮችም የአንድ ሰው፣ የአንድ ፓርቲ የፈላጭ ቆራጭነት ስርዓትን የሚያራምዱ ናቸው፡፡ የፖለቲካ ተቋማቱ እስከ አጥንታቸው ድረስ በዘለቀ የሙስና ነቀርሳ የበከቱ ናቸው፡፡ የይስሙላ ፓርላሜንታሪ ስርዓቶች አሏቸው፡፡ አቃቢያነ ህጎቻቸው በትምህርት፣ በማህበራዊ እና በሞራል ስብዕና አቅመቢስ የሆኑ ድሁር ወሮበላ ዘራፊዎች እና ጽናት የሌላቸው የእመኑልኝ የህግ መጽሐፍትን በብብታቸው ሸጉጠው የሚዞሩ የፓርቲ አባላት ናቸው፡፡ የፍትህ ስርዓቱ ከገዥው አካል አመራሮች የኋላ ኪስ የሚገኝ ስርዓት ነው፡፡ የጸረ ሙስና ኮሚሽኖች የፖሊቲካ ተቀናቃኞቻቸውን፣ በገዥው አካል ላይ የሚነሳሱትን ሰላማዊ አመጸኞችን ጨምሮ ለማጥቂያነት በእራስ የተሞሉ የርቀት አነጣጣሪ ሚሳይሎች ናቸው፡፡ የህግ የበላይነት የለም፣ ያለው የደናቁርት የዘራፊዎች ህግ ብቻ ነው፡፡

በአሁኑ ጊዜ EITI  በአፍሪካ እና በሌሎችም አገሮች ለዘመናት የሚዘልቅ የማዕድን ሙስና የተንሰራፋበት አዲስ ዓለም አቀፋዊ ስርዓት ለማንበር ዝግጅቱን አጠናቅቋል፡፡ ላለፉት አስርት ዓመታት EITI ያከናወናቸው ተግባራት እንግዲህ ይህንን ጉዳይ እውን ለማድረግ ነው፡፡ እውነት ለመናገር EITI  በእራሱ የሙስና ቡድን በሙስና የተዘፈቁ ገዥዎችን ለመከላከል የተቋቋመ ቡድን ነው፡፡ የአገራቸውን የተፈጥሮ ሀብት የዘረፉትን እና የመዘበሩትን ወሮበላ ዘራፊዎች መልሶ ለመዝረፍ የተቋቋመ ሰላማዊ ድርጅት ነው፡፡ ሁሉም በሙስና የተዘፈቁ ገዥ አካላት እንደገና ለመወለድ እና የEITIን ስርዎ መንግስት ለመቀዳጀት የሚከተሉትን ሂደቶች መከተል ይጠበቅባቸዋል፡፡ 1ኛ) የአባልነት መጠየቂያ ቅጹን መፈረም እና የEITIን የጥያቄ እና መልስ መዝሙሩን ደጋግሞ ማነብነብ፣ 2ኛ) መጠመቅ እና በ EITI ቄሶቹ መቀባት፣ 3ኛ) ቀደም ሲል ለተሰሩት ጥፋቶች በህዝብ ፊት ጥቂት ንስሀ የመግባት ተግባራትን ማከናወን፣ 4ኛ) ቀደም ሲል ለተፈጸሙ የሙስና ተግባራት ሁሉ ይቅርታ ማድረግ፣ 5ኛ) ከሙስና ወደ ንጹህነት እስኪመለሱ ድረስ የሶስት ዓመታት የዝግጅት ጊዜ መስጠት የሚሉት ናቸው፡፡

ለዘራፊ ገዥ አካላት ይህ ታላቅ ቅሌት ነው፡፡ የEITIን የከሀዲነት ባጅ ለማጥለቅ እና ከሙስና ምን ያህለ ነጻ እንደሆኑ በባዶ ኩራት በታጀለ መልኩ ለማሳመን በዝግጅት ላይ ናቸው፡፡  የEITI ባጅ በኢትዮጵያ ላሉት በሙስና የተዘፈቁ ዘራፊዎች የባዶ ዲስኩር የጉራ ችርቸራ  መብትን ያጎናጽፋቸዋል፡፡ የEITIን የአባልነት ፈቃድ በማግኘት በዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች እና በኢትዮጵያውያን/ት የዲያስፖራ ማህበረሰብ አባላት ላይ በእውነተኛነት ላይ ተመስርቶ የተገኘ ፈቃድ አስመስሎ ለመቅረብ በሸፍጥነት መጠቀሚያ ያድርጉታል፡፡ ” ሂዩማን ራይትስ ዎች አፍንጫችሁን ላሱ! የኢትዮጵያ የዲያስፖራ አፍንጫችሁን ላሱ! እዩ እንግዲህ ተመልከቱ እንደ አዳኝ ውሻ ጥርስ ንጹህ ነን እናም ከዚህ በላይ ማረጋገጫ የለም ይህንን ልናረጋግጥላችሁ እንችላለን!“:: የማዕድን ሙስናውን ከጥርጣሬም በላይ ከተጨባጩ ሁኔታ በላይ፣ ከቦርዱ በላይ እና ከህግ በላይ አጠናክረው ይቀጥሉበታል፡፡ የEITI የአባልነት ፈቃድ በመስጠት ለመስረቅ፣ የተፈጥሮ ሀብትን ታማኝነት በጎደለው የጮሌነት አካሄድ ጥቅምን ለማግበስበስ ለማይጠረጠሩ ባለሀብቶች በመስጠት የሞራል ልዕልና በጎደለው መልኩ ተበዳሪዎችን እና ለጋሽ ድርጅቶችን በመጭመቅ ሌላ ተጨማሪ ገንዘብ ማጋበስን የሚያስችል መብትን ይሰጣቸዋል፡፡

የEITI አባል ለመሆን የተዘጋጁት ደረጃዎቹ እና መስፈርቶቹ ጸጥ የማድረጊያ የማስመሰያነት ዘዴዎች ናቸው፡፡ እነዚህ ጸጥ የማድረጊያ ስልቶች ከውጭ የሚሰነዘሩባቸውን ትችቶች ለመሸበብ ብቻ አይደለም የተዘጋጁት ሆኖም ግን ከውስጥ ለሚነሱባቸው ሰላማዊ አመጾች ማዳፈኛ  እንዲሆኑ ጭምር እንጅ፡፡ EITI በአሰልች እና ተደጋጋሚነት ባለው የቢሮክራሲ ውጣውረድ የተተበተበ ፍሬከርስኪ የበዛበት የአባልነት መቀበያ መስፈርቶች፣ ተጠያቂነት እና ግልጸኝነት ያለው መሆኑን ከጉራ ባልዘለለ መልኩ ዲስኩር ሲያደርግ ይደመጣል፡፡ ማዳም ሾርት ግልጽ ደብዳቤ ብለው አዘጋጅተው በለቀቁት ደብዳቤ ላይ ለድርጅቱ እጩነት ለመብቃት “ከEITI ጋር አብሮ ለመስራት በግልጽ እና በቀላል መንገድ ለሲቪል ማህበረሰብ ድርቶች በቂ ምህዳር መኖር አለመኖሩ” ሁሉንም የህዝብ ግንኙት ስራዎች ሁሉ አፈር ድሜ አብልተውታል፡፡ ሌሎችስ በጣም አስመሳይ የሆኑ የባለስልጣን መስፈርቶች እንዴት ይታያሉ? እንዲሁ ዝም ብሎ የባህላዊ ጭፈራ እና ዳንስ ነውን?

በማንኛውም ትክክለኛ በሆነ መለኪያ በኢትዮጵያ ያለው ገዥ አካል የEITI አባልነት ተቀባይነት ማግኘት የድርጅቱ መስፈርቶች ባዶ እና ወና መሆናቸውን ያመላክታል፡፡ EITI የእራሱን ቡድን ለመቀላቀል “አንድ መንግስት የድርጅቱ አባል ሲሆን ምን መስራት እንዳለበት እምነቱን የሚገልጽ እና EITIን ለማጠናከር ያለውን ጽኑ የሆነ መግለጫ አዘጋጅቶ ማቅረብ ይጠበቅበታል፡፡” እውነት! ትልቅ ነገር! በመቀጠልም መንግስት “የEITIን ተግባራት ለማከናወን ሃላፊነት ያለው ከፍተኛ ባለስልጣን መሾም አለበት፡፡” እርግጥ ነው ሙሰኛ አሻንጉሊት የድርጅቱን ተግባራት መከናወናቸውን የሚከታተል ሌላ ሙሰኛ አሻንጉሊት ይሾማል፡፡ መንግስት “ከሲቪል ማህበረሰቡ ጋር መስራት ይጠበቅበታል፡፡” የትኛው ሲቪል ማህበረሰብ? ምንም ችግር የለም፡፡ ሙሰኛ ዘራፊዎች በሀገሮቻቸው ውስጥ እውነተኛ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶችን ስለሚያጠፏቸው እነዚህ ዘራፊዎች ለእነርሱ የሚበጁትን የይስሙላ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች መቀፍቀፍ እንዲችሉ የፈቃድ ሰርቲፊኬቱን EITI ይሰጣቸዋል፡፡ ለዚህም ነው በኢትዮጵያ ያለው ገዥ አካል የ “ኢትዮጵያ ብሄራዊ የጋዜጠኞች ህብረት” የሚል ሆድአደር ተለጣፊ ድርጅት በመፍጠር ሌሎችን እያሳደደ በማጥፋት ላይ ያለው፡፡ እንዲህ ያለ ቀልድ!

ከመሀል አዲስ አበባ ወጣ ብሎ የሚገኘው የአቶ መለስ የቃሊቲው የእስረኞች የማጎሪያ ማዕከል እውነተኛ ለፍትህ እና ለሀቅ የቆሙ ዕውቅናን ያተረፉ ጋዜጠኞች እንዲሁም በዓለም አቀፍ ደረጃ ውድ እና ላቅ ያለ ደረጃ ያላቸውን ዓለም አቀፍ ሽልማቶች እየተቀበሉ የሚገኙት በርካታ ጋዜጠኞች እስክንድር ነጋ፣ ርዕዮት ዓለሙ እና ውብሸት ታዬ የመሳሰሉትን ጀግና ጋዜጠኞች ውጦ የምጻት ቀኑን የሚጠባበቅ የሰላማዊ ዜጎች የማሰቃያ ተቋም ነው፡፡ እስክንድር ነጋ በቅርቡ በህይወት በተለዩት በአቶ መለስ ዜናዊ ላይ ትችት በማቅረቡ እና በአረቡ ዓለም እየተካሄደ ባለው የጸደይ አብዮትን በማስመልከት በሰጠው ትንታኔ ብቻ ለ18 ዓመታት በእስር ቤት እንዲማቅቅ ያለምንም ሀፍረት ተበይኖበታል፡፡ ርዕዮት ዓለሙ እና ውብሸት ታዬ በየሳምንቱ በሚወጣ መጽሄት ላይ ሀሳባቸውን በመግለጻቸው ብቻ እያንዳንዳቸው በ14 ዓመታት እስር እንዲቀጡ በማንአለብኝነት በይስሙላው/የዝንጀሮ ፍርድ ቤት ህሊናየለሽ ውሳኔ ተበይኖባቸዋል፡፡

ከተለጣፊው “ከኢትዮጵያ ብሄራዊ የጋዜጠኞች ህብረት” ስለኢትዮጵያ የማዕድን ዘርፍ የተጠያቂነት እና ግልጸኝነት ትክክለኛ መረጃ ለማግኘት መጠበቅ ማለት የዶሮዎችን መጠለያ ቤት እንዲጠብቅ ኃላፊነት ከሚሰጠው ቀበሮ አንድም ዶሮ ላለመጥፋቱ ትክክለኛ የሂሳብ ሪፖርት እንዲያቀርብ መጠየቅ እንደማለት ነው፡፡ በEITI ገዥ አካሎች መሰረታዊ ሀሳብ መሰረት ህብረተሰቡን ያለምንም ተጽዕኖ የበላይ ተመልካችነት እና የተቆጣጣሪነት ስልጣን በመስጠት በቀጥታ ተሳታፊ በማድረግ በማዕድን እና በተፈጥሮ ጋዝ ዘርፉ ላይ ትክክለኛ እና በዘርፉ ሊረጋገጥ የሚችል መረጃን አዘጋጅቶ የማውጣት ስራን በማቀላጠፍ ሂደቱን የማሳለጥ ተግባራትን የማከናወን ስራ ነው፡፡ የዚህ ሁሉ የመጨረሻው ግቡ ደግሞ “ከተፈጥሮ ሀብት ተፈብርኮ የሚገኘው የምርት ገቢ በትክክል ያለምንም ሙስና ለህዝቡ ጥቅም እንዲውል መራጋገጫ የሚሰጥ ነው፡፡”

መረጃን በተመለከተ በኢትዮጵያ ያለው ገዥ አካል አስቀያሚ የመረጃ መቀቀያ ቶፋ አለው፡፡ “የአቶ መለስ ዜናዊ ምዕናባዊ የምጣኔ ሀብት“ እና “የአቶ መለስ ዜናዊ የውሸት የምጣኔ ሀብት” በሚሉ ርዕሶች ሳቀርብ እንደነበረ ሁሉ የአቶ መለስ ዜናዊ አገዛዝ በእርሳቸው አመራር ኢትዮጵያ አስር ዓመት  ሙሉ ያለምንም ማቋረጥ “ባለሁለት አሀዝ የኢኮኖሚ መጣኔ ዕድገት አስመዘገበች” በማለት ለፖለቲካ ፍጆታ ሲባል ብቻ የውሸት መረጃ በመረጃ መቀቀያው ቶፋ እየታጨቀ የሀሰት መረጃ ሲሰራጭ ቆይቷል፡፡ እውነታው ግን ላም አለኝ በሰማይ ነው፡፡ ብዙሀኑ የኢትዮጵያ ህዝብ አይደለም በቀን ሶስት ጊዜ አንድ ጊዜ እንኳን ለመብላት እየተቸገረ ነው ያለው፡፡

በጣም የሚያስደንቀው ነገር ደግሞ አቶ መለስ በብልጣብልጥነት የእራሳቸውን የቅጥፍና የኢኮኖሚ የዕድገት መረጃ አሀዝ ለዓለም ባንክ እና ለዓለም አቀፉ የገንዘብ ድርጅት የመመገባቸው ጉዳይ ይህንንም ተከትሎ እነዚህ ዓለም አቀፍ ተቋማት የእርሳቸውን ጥሩንባ የመንፋታቸው ጉዳይ ነው፡፡ እነዚህ ዓለም አቀፍ ተቋማት ከማንም በተሻለ መልክ ግንዛቤው ያላቸው ቢሆንም የዓለም ባንክ እና የዓለም አቀፉ የገንዘብ ተቋም ከቅርብ ጊዜ ጀምሮ ታላቅ እና ድፍረት የተሞላበት የውሸት የኢኮኖሚ ዘገባ በማቅረብ ወንጀለኛ ገዥ አካላት ዕኩይ ድርጊታቸው የሀሰት ዘገባዎችን እንዲያቀርቡ እየገዟቸው ይገኛሉ፡፡

በኢትዮጵያ ያለው ገዥ አካል  በEITI የቀሚስ ጉንፍ ውስጥ ተወሽቆ በማዕድኑ ምርት እና ገቢ ሁሉምን ዓይነት የሀሰት የመረጃ አሀዞችን በመቀፍቀፍ እንዲሁም በሚሊዮኖች የሚቆጠር አንጡራ የሀገሪቱን ሀብት ወደ ውጭ በማሸሽ ውጭ አገር በሚገኙ የግል የባንክ ሂሳቦቻቸው ላይ በማስቀመጥ ላይ እንደሆኑ እና እንደዚህ ያሉ ተመሳሳይ የማታለል ድርጊቶችን በመፈጸም ላይ እንደሚገኙ የክርክር ጭብጤን ላቀርብ እችላለሁ፡፡ ወደፊት “በEITI ጋሻጃግሬነት እየተካሄደ ያለ የኢትዮጵያ የማዕድን ሙስና ተምኔታዊ የመረጃ አሃዞች” በሚል ርዕስ ስር ትችት አቀርባለሁ የሚል ዕቅድ አለኝ፡፡

EITI  ጥሩ የሚመስሉ መስፈርቶችን በማቅረብ ሆኖም ግን በአፍሪካ እና በሌሎች ታዳጊ አገሮች ለሚካሄዱት የአምራች ኢንዱስትሪዎች ሙስና የህጋዊነት ሽፋን በመስጠት የህጋዊነት ሀሳባዊነትን፣ ታማኝነትን ግልጽነት እና ተጠያቂነት ለመፍጠር ዓላማ ያደረገ ነው፡፡ EITI “የድብቅ ቴክኖሎጅን” የሚጠቀም በመሆኑ በአፍሪካ እና በሌላው ዓለም ያሉ በሙስና የተዘፈቁ ገዥ አካላት ያለምንም ስጋት እና ጥርጣሬ የህዝቦቻቸውን ሀብቶች ለመዝረፍ ሲሉ ተቋሙን መቀላቀል ይፈልጉታል፡፡ EITI እምነት ከማይጣልባቸው፣ በሙስና ከተዘፈቁ እና አስጸያፊ ባህሪያትን የተላበሱ፣ እንዲሁም ከብዙ ጊዜ ጀምሮ በዓለም መድረክ ላይ በመጀመሪያ እምነቱን በማግኘት በኋላ የሚከዳበት ዓይነት ጨዋታ ከሚደረግባቸው ድርጅቶች መካከል አንደኛው ነው ማለት ይቻላል፡፡

ሁለት ጊዜ ይቅርታ መጠየቅ እና አንዱን በጽናት መያዝ፣

“የማዕድን ሙስና በኢትዮጵያ፡ ለማዳም ክላሬ የተሰጠ መልስ” በሚለው የመጀመሪያው ትችቴ ላይ ማዳም ክላሬ የኢትዮጵያን የEITI አባል መሆን አስመልክቶ የዲያስፖራ ማህበረሰብ አባላት ከጉዳዩ ውጭ እንዲሆኑ ስላደረጓቸው አሰልች ቀኖናዊ ህጎች ለዲያስፖራው ማህበረሰብ ይቅርታ እንዲያቀርቡ ሀሳብ አቅርቤ ነበር፡፡ ማዳሟ “የቦርድ አባላቱ የኢትዮጵያን የተባበረ የሲቪል ማህበረሰብ ድምጽ እንጅ የተቃዋሚ ዲያስፖራ ድምጾችን መስማት እንደሌለበት ተማጽዕኖ አቅርበው ነበር፡፡” ውጤታማ በሆነ መልኩም የኢትዮጵያ ዲያስፖራ ድምጽ መዘጋት  እንዳለበት ሞግተዋል፡፡

“ግልጽ እና የተባበረው የኢትዮጵያ ሲቪል ማህበረሰብ” የማዳም ሾርት ፍጹም የሆነ ምዕናባዊ የሆነ እና የተረጋጋ ስሜት እንዳይኖር በማድረግ ዓላማ ላይ የሚሽከረከር ሆኖ ይገኛል፡፡ ትክክለኞቹ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ከዓመታት በፊት ጀምሮ ታፍነው ተሸብበው  ይገኛሉ፡፡ ሆኖም ግን ማዳም ሾርት በአንድ ወይም በሌላ ምክንያት በኢትዮጵያ የሲቪል ማህበረሰብ የሌለውን አለ የሚል ቅዠት ለማንበር ይፈልጋሉ፡፡ ምናልባትም የእርሳቸው የስሜት ጓደኛ እንደሆኑት እንደ አቶ መለስ ዜናዊ የመኝታ ጊዜ ትረካዎችን መናገር መውደድ አለባቸው፡፡ እኔ በትረካዎች ላይ በእርግጠኝነት ትዕግስት ማድረግን እከተላለሁ፣ እንደ ዶ/ር ሰውስ ተረት:- “ ተረት ተረት የላም በረት: አንድ ዓሳ፡፡ ሁለት ዓሳዎች፡፡ ቀይ ዓሳ፡፡ ሰማያዊ ዓሳ፡፡” ተረት ተረት አንድ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅት፡፡ ሁለት የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች፡፡ ሰማያዊ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅት፡፡

በእርግጠኝነት ለተቀደሰ ተግባር፣ የተከበረ እና ሩህሩህነት የተንጸባረቀበት ሀሳብ ሲባል ማዳም ሾርት ለዲያስፖራ ኢትዮጵያውያን/ት የይቅርታ ደብዳቤ ማስገባት ይኖርባቸዋል የሚል ተስፋ ነበረኝ፡፡ ምናልባትም “ከተናገርኩት ውጭ የስህተት ግንዛቤ ተይዟል ይቅርታ” ሊሉ ይችሉ ይሆናል፡፡ እንደ ቆንጆ የህዝብ ግንኙነት ስራ በእርግጠኝነት ላይሉም ይችላሉ፡፡ ማዳም በእርሳቸው የተዛባ ጥላቻ  ሰበብ የጥቃት ሰለባ ለሆኑት ወገኖች ይቅርታ ለመጠየቅ ለጋስነቱ ያላቸው አይመስልም፡፡ የዘመኑን የወጣቶችን ንግግር ለመጠቀም ማዳም ሾርት ሰዎችን በመበጥበጥ ከዘራፊዎች ድንበር ተርታ ጋር የሚያመሳስል የረዥም ጊዜ እውቅና አላቸው፡፡ ማዳም ሾርት በብርሀን ፍጥነት ተናዳጅነታቸው እና ግንፍልተኝነታቸው ይታወቃሉ፡፡ ሪቻርድ ዶውደን የተባለው የእንግሊዝ ታዋቂ ጋዜጠኛ እ.ኤ.አ በ2011 ከማዳም ሾርት ትረካውን እንዲህ አቅርቦታል፡፡ “በአንድ ወቅት በአውሮፕላን ላይ ቃለ መጠይቅ እያደረግሁላቸው ሳለ እና ስለሩዋንዳ የሰብአዊ መብት ሁኔታ ትኩረት በመስጠት ጥያቄዬን ሳቀርብ ማዳሟ እኔን ለመወርወር በሚያስችል ዓይነት ሁኔታ አስፈራሩኝ፡፡ በዚያን ወቅት በጊኒ የአየር ክልል ላይ ስለነበርን ከዚያ በኋላ አቆምኩ፡፡ አሁን ደግሞ የተዋበ፣ ሰላም እና መረጋጋት በሰፈነበት በለንደን የጋራ ሀብት ክለብ ተገናኘን፣ እናም ማዳሟ እርጋታ የሚታይባቸው እና ሀሳብ የሚሰጡ ሆኖም ግን በማንም ዘንድ ጠንካራ ትችት የሚያቀርቡ የሚያደርጉትንም በብልኃት መያዝ የማይችሉ ሆነው ነው ያገኘኋቸው፡፡“ ማዳም ሾርት ቀልድ አያውቁም! ቶኒ ብሌር ሃሰባቸውን እንዳይገልጹ ለማድረግ በሀይል አፋቸውን ያስይዟቸው ነበር፡፡ (ብሌር የተናገሩት አያስደነቅም:- ”እንደተዋረደች እና ሀሳቧን እንዳትገልጽ በኃይል እንደተያዘች ሚስት ነው የተሰማኝ፡፡” ያሉት ሲያመናጭቁአቸው:: ይህ አካሄድ የማዳም ሾርት አጭሩ ጎዳና ነው! ቢሆንም ለማዳሟ ክብር እሰጣቸዋለሁ፡፡ ለሚያምኑት ይቆማሉ: ይዋጋሉ:: በኢትዮጵያ በስልጣን ላይ ላሉት ገዥ ዘራፊዎች በጽናት ይቅርታ የሚያቀርቡ ሴት ናቸው፡፡

የኢትዮጵያ የዲያስፖራ ማህበረሰብ አባላትን ይቅርታ መጠየቅ አስፈላጊ አይደለም፡፡ ሆኖም ግን ማዳም ሾርት በድርጅታቸው ያሉትን የሰቪል ማህበረሰብ ድርጅት ተወካዮችን ማለትም ዓሊ ኢድሪሳን፣ ንዋዲሺን ጂን ክላውዲ ካቴንዴን እና ሌሎችን የከፈለህን አትም አባላት ይቅርታ ጠይቀዋል፡፡ ይህንን በጥብቅ እጠይቃለሁ! ማዳሟ “በግልጽ ደብዳቢያቸው” ፍትህዊነትን በጣሰ መልኩ አስደናቂ ተዋንያን በመሆን በዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች ላይ አምባርቀውባቸዋል፡፡ “የተለየ ፍላጎት ያላቸው ቡድኖች ጠንካራ ድምጾችን በማሰማት ተጽዕኖ ለመፍጠር የሚደረግ ጥረት እንዳለ እና እንዲያውም የሰሜን ደቡቡን እንዲወስንለት በታቀደ ዘይቤ የሚመሩ ናቸው በማለት ክስ አቅርበውባቸዋል፡፡” የኢትዮጵያ ገዥው አካል የEITI አባል እንዳይሆን ተቀዋሚዎች ተቃውሞ በማሰማት የEITIን ዕድል ተፈታትነዋል በማለት ማዳሟ ጩኸታቸውን አሰምተዋል፡፡

ኢድሪሳ፣ ንዋዲሺ እና ካቴንዴን በማክበር ለማዳም ሾርት ግልጽ ደብዳቤ ግልጽ ምላሽ ሰጥተዋል፡፡ እንዲህም ብለዋል፣ “የኢትዮጵያ የEITI የአባልነት ጥያቄ በቀጣናው ስብሰባ እዲቀርብ በአጀንዳችን ውስጥ አልነበረም በእርግጥ ይህ ጉዳይ የከባቢ ሁኔታ ግምገማዎችን እያደረግን ባለንበት ሁኔታ ነው የመጣው፡፡“ በወቅቱ ሁለት ገዥ ሀሳቦች ተነስተው አንደኛው በመቃወም ሁለተኛው ደግሞ በመደገፍ ክርክር እንደነበር ገልጸዋል፡፡ “ገለልተኛ” በሆነ መልኩ ማዳሟን እንዲህ በማለት ሞግተዋል፣ “ኢትዮጵያ የEITI አባል እንድትሆን ግልጽ አቋም በመያዝ  ወገንተኝነት አሳይተዋል፣ ከገለልተኝነት መርህ ጋር በተጻረረ መልኩ በድርጅቱ ሊቀመንበርነትዎ ላይ ጥያቄ ሊያስነሳ የሚችል ድርጊትን ፈጽመዋል፡፡ የድርጅቱ ታማኝ የመሆን ጠቀሜታ መሰረት የሚለካው በዚህ ጠቃሚ መርህ ነው፡፡” በዚህ አስፈሪ ግልጽ ደብዳቤ እንቆቅልሽ የሆነባቸው መሆኑን ገልጸዋል፡፡ “በዚህ ጉዳይ ላይ ግልጹ ደብዳቤ ለተውሰኑ ጥቂት ሰዎች ማሳወቅ ሲገባ ለምን ለህዝብ ይፋ እንደተደረገ ግልጽ አለመሆኑን ለመጠቆም እንፈልጋለን… እንደዚሁም የእኛም ደብዳቤ እርስዎ ለህዝብ ለአደባባይ እንዳቀረቡት ሁሉ በEITI ድረ ገጽ ላይ እንዲታተም እንጠይቃለን፡፡ ከዚህም በተጨማሪ በሲቪል ማህበረሰብ ተወካዮች ዓለም አቀፍ ድረ ገጽ ለጥምረት አባሎቻችን በሙሉ ሊለቀቅ ይገባል፡፡“ የሚል ነው፡፡

ማዳም ሾርት ለኢድሪሳ፣ ንዋዲሺ እና ካቴንዴ በቀጥታ ሳይሆን በጸሐፊያቸው በጆናስ ሞበርግ በኩል ምላሽ ሰጥተዋል፡፡ የተሰጠው መልስ በቁስል ላይ ጨው  መነስነስ ያህል ነበር፡፡ ማዳሟ በግልጽ ደብዳቢያቸው ለኢድሪሳ፣ ንዋዲሺ እና ካቴንዴ ደብዳቤ መጻፉ ችግር እንደሌለባቸው በመጮህ የተናገሩ ሲሆን ቀደም ሲል የዓለም ማህበረሰብ ከማወቁ በፊት መደረግ እንደነበረበት ተናግረዋል፣ ሆኖም ግን በኋላ ደፍረው ሲመልሱ አንዴት ተደርጎ!? በተለመደው ቦታቸው አርፈው እንዲቀመጡ ይጠበቅባቸዋል፡፡ ሞበርግ ይህንን ቆሻሻ ስራ የተሰጠው ሰው ነው፡፡ እኔ በግሌ የሚከተለውን ሳነብ እንደተዋረድኩ እቆጥረዋለሁ፣

“ማዳም ክላሬ ለእናንተ ደብዳቤ ምላሽ እንድጽፍ ጠይቀውኛል፡፡ ያቀረባችኋቸው ነጥቦች በሙሉ ማስታወሻ ተይዞባቸዋል፣ የሊቀመንበሯን ገለልተኛነት ተብሎ ከሚጠራው ነጥብ በስተቀር፡፡ ለጂን ክላውዴ እንደገለጽኩት ሁሉ ሊቀመንበሯ ገለልተኛ እንዲሆኑ አይጠበቅባቸውም፡፡ እንደማንኛቸውም የእኛ ባለድርሻ አካላት ተወካዮች ሁሉ ገለልተኛ መሆን እንዳለባቸው አይነት በመሆን ሊሰሩ አይችሉም፡፡ ሊቀመንበሯ EITIን ነው የሚያገለግሉት ምክንያቱም በድርጅቱ መርሆዎች ላይ እምነት ስላላቸው ነው፡፡ እነዚህን መርሆዎች የመጠበቅ ኃላፊነት እና የEITIን ጥቅም ማስጠበቅ አለባቸው፣ እናም ለእናንተ ደብዳቤ በጻፉበት ወቅት ያደረጉት ነገር ቢኖር ይህንኑ ነው፡፡ በደብዳቢያቸው ላይ የሊቀመንበሯን ሚና የሚጥስ ነገር አልታየም፡፡”

ኢድሪሳ፣ ንዋዲሺ እና ካቴንዴ ከክብርትነታቸው በቀጥታ የሚጻፍ ደብዳቤ እንደክብርቷ አመለካከት ከሆነ አይመጥናቸውም፡፡ በሌላ አገላለጽ የማዳሟን ክብር ዝቅ የሚያደርግ ነገር ነው፡፡የሞበርግን ደብዳቤ በድጋሜ ሳነበው በጫካ እንደሚኖረው ባለረዥም ጅራት ቆርጣሚ አውሬ በንዴት ብግን ነው ያልኩት፡፡ ማዳም ሾርት ምን ያህል ደፋር መሆናቸውን የሚያሳየው በጸሐፊው አማካይነት ምላሽ የሰጡ መሆናቸውን ስናስተውል ነው! ማንም ጭራቃዊነት የሰራው እርሳቸው አይደሉምን?! በፍጹም የማለት ሞገስ ሊኖራቸው አይችልምን! ቀላሉ ዘዴ በጸሐፊያቸው አማካይነት የማርቀቅ እና እርሳቸው ፈርመው መላክ ነው፡፡ በግልጽ ለመናገር ማዳም ሾርት ለኢድሪሳ፣ ንዋዲሺ እና ካቴንዴ ግልጽ መልዕክት ማስተላለፍ ፈልገዋል፡፡ ማን አለቃ እንደሆነ እና አጠቃላይ ሁኔታውን ለማሳወቅ ፈልገዋል፡፡ እርሳቸው አለቃ ናቸው፣ ስለሆነም ስለማንኛውም ነገር ደንታ የላቸውም፡፡ እንደዚሁም ደግሞ ማዳም ሾርት ስለኢድሪሳ፣ ንዋዲሺ እና ስለካቴንዴ ጉዳይ ደንታ የላቸውም!

ስለሰው ልጅ ስብዕና፣ ክብር እና ሞገስ ስል በኢድሪሳ፣ ንዋዲሺ እና ካቴንዴ ስም እኔ ይቅርታ እጠይቃለሁ፡፡ ከእነዚህ ሰዎች ጋር ተገናኝቸ ወይም ደግሞ ተነጋግሬ አላውቅም፡፡ ሆኖም ግን እንደ አንድ አፍሪካዊ ወገኖቼ የእነርሱ ውርደት የእኔም ውርደት እንደሆነ እንዲገነዘቡልኝ እፈልጋለሁ፡፡ በእንደዚያ ዓይነት አያያዝ ሲስተናገዱ ስመለከት እንደ አፍሪካዊ የእኔ ኩራት ጉዳት ደርሶበታል፡፡ ሆኖም ግን እንዲያውቁልኝ የምፈልገው ነገር ቢኖር ጠንካራ ኩራት እና ኃይል ይሰማኛል፡፡ ለማዳም ሾርት አስደንጋጭ ግልጽ ድብዳቤ የሰጡት ምላሽ የአስተዋይነት፣ የምክንያታዊነት እና የተለምዷዊ በጎ ምግባር ተምሳሌት ነበር፡፡ እነዚህ አፍሪካውያኑ በምላሻቸው ላይ ቁጥብነትን፣ ባለሞያነትን፣ታጋሽነትን እና ታማኝነትን አሳይተዋል፡፡ እንደዚሁም ደግሞ “አፍሪካዊ ትውልዶቻቸው እሺ! አቤት ወዴት! እርስዎ እንዳሉት ጌታዬ!” እያሉ ስብዕናቸውን ዝቅ ማድረግ በፍጹም እንደሌለባቸው በተጨባጭ አሳይተዋል፡፡ ማዳም ሾርት እና መሰሎቻቸው አዲሱ የአፍሪካ ትውልድ ለማንም ሎሌ እንደማይሆን ሊገነዘቡ ይገባል፡፡ በአሁኑ ጊዜ ሰውን ባለቃነቱ ብቻ “አዎ አዳኙ ጌታዬ” የሚባለው ተረት ተረት ጊዜው ያለፈበት እና ያፈጀበት ዘመን ላይ ነን፡፡ ሁላችንም አፍሪካውያን በጀግኖቹ ኢድሪሳ፣ ንዋዲሺ እና ካቴንዴ ልንኮራ ይገባል፣ ምክንያቱም ክብርን በደፈጠጠ እና ባዋረደ ጭራቃዊ መንፈስ ላይ የብዕር ጦራቸውን በመስበቅ ክብር እና ሞገስን እንድንቀዳጅ አስችለውናል፡፡ በከፍተኛ ደረጃ የፈጸሙት ተግባር ነው፡፡ ይሄ ነው ጀግኖች! እናደንቃችኋለን ኢድሪሳ፣ ንዋዲሺ እና ካቴንዴ፡፡

በተጨማሪም ማዳም ሾርት በተደጋጋሚ በተናገሩት አቁሳይ እና ከስልጣን ገደባቸው ውጭ በመሄድ ላሳዩት ትዕቢት በተቀላቀለበት ድንፋታ ስሜታቸው እንዳይጎዳ መጽናናትን እንዲያደርጉ እማጸናለሁ፡፡ ከሁሉም በላይ ደግሞ ማዳም ሾርት በቅርቡ በህይወት የተለዩት የአቶ መለስ ዜናዊ አምላኪ ናቸው፡፡ እ.ኤ.አ በኤፕሪል 2013 ማዳም ሾርት በአንድ የመታሰቢያ በዓል ላይ በመገኘት አቶ መለስ “ታላቁ” ሰው በማለት አድናቆታቸውን ገልጸዋል፡፡  እንዲህም ብለዋል፣ “አቶ መለስ በህይወት ዘመኔ ካየኋቸው ሁሉ የመጠቀ እውቀት ያላቸው ፖለቲከኛ ናቸው” በማለት አሞካሽተዋቸዋል፡፡ (ቶኒ ብሌር፣ ጎርደን ብራውን፣ ሃሬት ሃርማን፣ ኢድ ሚሊባንድ፣ ዴቪድ ካሜሩን፣ ጆህን ሜጀር፣ ታቼርን ቅርጫት ደፉባቸው፡፡ ማዳም ሾርት ደስ ያላልዎትን የሚያስጨንቀዎን ነገር መግለጽ ይችላሉ!) እኔ በበኩሌ “አቶ መለስ ሁሉን ነገር አዋቂ” መሆናቸውን አላውቅም፣ ይልቁንም አነጣጥሮ ገዳይ እና አስገዳይ ተራ እርባናቢስ ለሰው ክብር የሌላቸው ዉዳቂ የነበሩ ለመሆናቸው ቅንጣት ያህል ጥርጣሬ የለኝም፡፡ እስቲ አካባቢያችሁን ተመልከቱ፣ ሁሉም ጭራቸውን ይቆላሉ፡፡

አቶ መለስ እንደ ማዳም ሾርት ሁሉ እርሳቸውን የተቃወሟቸውን ወይም በእርሳቸው ላይ ትችት ያቀረቡትን ሁሉ “ድራሻቸውን የሚያጠፉ” በእብሪት የተሞሉ ሰው ነበሩ፡፡ የእርሳቸውን ተቀናቃኞች በተደጋጋሚ “ደደቦች”፣ “ቆሻሾች”፣ “የጭቃ ጅራፎች”፣ “ስግብግቦች” እና “ለምንም የማይጠቅሙ እርባና ቢሶች” በማለት ይፈርጇቸው ነበር፡፡ እንደዚሁም በሰለጠነ ህብረተሰብ አጠራር መሰረት ደግሞ ለመጥራት ጸያፍ የሆኑ ስሞችን ይለጥፉ ነበር፡፡ አቶ መለስ በኢትዮጵያ ታሪክ የመጀመሪያዋ ሴት ሊቀመንበር የነበሩትን ወ/ት ብርቱካን ሚደቅሳን ወደ እስር ቤት ወርውረው ለብቻ በአንድ ክፍል ውስጥ እንዲታሰሩ ካደረጉ በኋላ እንቅስቃሴ ባለማድረጓ ምክንያት የመወፈር ነገር ይታይባታል የሚል ምጸት አሰምተዋል፡፡ አቶ መለስ በፓርላሜንት ጉባኤ ላይ የሚገዳደሩ ጥያቄዎችን በማንሳት ወይም ሌላ ለየት ያለ አካሄድ እንዳለ ለማሳየት ሀሳብ የሚያቀርቡ ተወካዮችን በማዋረድ እና በመዘለፍ በሚፈጽሟቸው ጭራቃዊ ድርጊቶቻቸው ይደሰቱ እና እርካታን ያገኙ ነበር፡፡ የእርሳቸው ሰውን አሳንሶ የመመልከት፣ ምጸታዊ ንግግር፣ እና ለሚጠየቋቸው ጥያቄዎች የሚሰጧቸው ንቀት የተሞሉባቸው መልሶች በጣም አዋራጅ እና የተጠየቁ ጠቃሚ ነገሮችን ነቅሰው በማውጣ መልስ እንዳያገኙ የመዝለል ሁኔታዎች አንዳንድ ድፍረት ያላቸው የተቃዋሚ ፓርቲ አባላት ተወካዮች በድፍረት ለሚያቀርቧቸው ጥያቄዎች የሚሰጧቸው ምላሾች እና የመድረክ ተውኔቶች ነበሩ፡፡ እ.ኤ.አ በሜይ 2010 የተደረገውን ሀገር አቀፍ ምርጫ 99.6 በመቶ የተገኘው የድምጽ ውጤት በመጭበረበሩ ምክንያት የተገኘ መሆኑን የአውሮፓ ህብረት የታዛቢዎች ቡድን አቶ መለስን ከእውነታው ጋር አፋጥጠው ሲይዟቸው አቶ መለስ የአውሮፓ ህብረት የታዛቢዎች ቡድንን ዘገባ “ወደ ቅርጫት መጣል ያለበት ቆሻሻ ነው” በማለት በጅምላ አውግዘዋቸዋል፡፡ ምን ማለት እችላለሁ?  እራስን በአምላክነት ሰይሞ ተከታይ እንዲኖር መፈለግ!

ማዳም ሾርት የEITIን መርሆዎች እሰከብረዋል ወይስ ደግሞ በኢትዮጵያ ያለው ገዥ አካል ተሟጋች/ወኪል ነበሩ?

ማዳም ሾርት በሞበርግ አማካይነት ለኢድሪሳ፣ ንዋዲሺ እና ካቴንዴ በሰጡት ምላሽ ለኢትዮጵያ ወገንተኛ ያልነበሩ ብቻ ሳይሆን የEITIን መርሆዎች ለማስጠበቅ እና ለEITI ጥቅም ተግተው በመስራት ኃላፊነታቸውን እንደሚወጡ የሚገልጽ ነበር፡፡ እርግጠኛ ነዎትን?

ማዳም ሾርት “የEITIን መርሆዎች አስጠብቀው” ነበር ወይስ ደግሞ በኢትዮጵያ ላለው ገዥ አካል ወግነው ነው ይህን የሚከተለውን ግልጽ ደብዳቤ የጻፉት የሚለውን ማየት ለግንዛቤ የበለጠ ይረዳል፡፡

በኢትዮጵያ ያለው የሲቪል ማህበረሰብ ሁኔታ ከሌሎች በርካታ አገሮች የከፋ ነው የሚለውን አልቀበለውም፡፡

በኢትዮጵያ ጉዳይ ላይ ያለው ውይይት ጠቀሜታ በሌለው መንገድ የተለየ ፍላጎት ባላቸው እና ሙሉ ትርጉም ባለው “የሰሜኖች ለደቡቦች መናገር አለባቸው በሚለው የአሰራር ዘየ” በተገመደ ጠንካራ ድምጽ ተጽዕኖ ስር የወደቀ በመሆኑ ላይ መናገር አለብኝ፡፡

የአትዮጵያን የአባልነት ጥያቄ ውድቅ ማድረግ ማለት የኢትዮጵያ ሲቪል ማህበረሰብ የትም እንዳይሄዱ ማድረግ ማለት ነው፡፡

ከኢትዮጵያ የዲያስፖራ ማህበረሰብ ተቃውሞዎችን ከመስማት ይልቅ በኢትዮጵያ ግልጽ እና የተባበሩ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶችን ድምጽ መስማት ያለብን በመሆኑ ላይ ያለኝን እምነት መግለጽ እፈልጋለሁ፡፡

በጥሩ ሁኔታ መስራት የሚችሉ በጣም ጠንካራ የሆኑ ሌሎችን የአፍሪካ አገሮች ሊቀላቀሉ የሚችሉ የሲቪል ማህበረሰብ ቡድኖች እንዳሉ ከሀሳባዊነት በራቀ መልኩ ምንም ዓይነት ጥርጥር የለኝም

አንድ ዓይነት ወጥነት የሌላቸው መስፈርቶች መኖርም ሌላው ታላቅ ችግር ነው፡፡ ለምሳሌ በሀገሬ የቅዱስ ፓውሎስ ካቴድራል ውጫዊ ክፍልን በኃይል የተቆጣጠሩትን ተቃዋሚዎች ማባረረን አስመልክቶ የሚነገር ጉምጉምታ አለ፡፡ የጓንታናሞ መኖር እና ማሰቃየትን የመተግበር ሁኔታ አስመልክቶ ዩናይትድ ስቴትስ ጉዳይ ለአባልነት ጥያቄ ሲቀርብ አልተነሳም፡፡

EITI የዘመቻ አድራጊዎች መሳሪያ ተደርጎ የሚታይ ከሆነ ውጤታማ እና ድጋፍ የሚኖረው ሊሆን አይችልም፡፡

ጎራዴው ለምን ማጥቂያነት ይውላል?

ማደም ሾርት ገዠው አካል የEITI አባል መሆን እንዲችል ጉሮሮ ለጉሮሮ በመተናነቅ ከፍተኛ ተጋድሎ አድርገዋል፡፡ በግልጽ ድብዳቢያቸው በኢትዮጵያ ያለው ገዥ አካል አባል እንዲሆን ሽንጣቸውን ገትረው የውትወታ ተግባራቸውን አከናውነዋል፡፡ ማንም ሽንጡን ገትሮ ላመነበት ጉዳይ ትጋድሎ የሚያደርግን ሰው በሀሳብ የማንግባባ ቢሆንም እንኳን አከብራለሁ፡፡ ማዳም ሾርትም ላመኑበት ጉዳይ በጽናት መቆማቸውን አደንቃለሁ፡፡ ሆኖም ግን እደነቃለሁ፣ በእርግጥም በጣም እደነቃለሁ! ማዳሟ ላደረጉት የጽናት ተጋድሎ ዋጋቸው ምን ሊሆን ይችል ይሆን? በኢትዮጵያ ላሉ ዘራፊዎች ማዳም ሾርት ያደረጉት ተጋድሎ ዋጋ ምን ያህል ይሆን? የማዳም ነብስ ዋጋው ምን ያህል ይሆን?

በእርግጠኘነት ስለEITI ከልብ የሚቆረቆረው ማን ነው?

EITI፣ CCC፣ EEITI  ማንም ይሁን! ማን ነው ያገባኛል የሚለው? ማን ነው ትኩረት አድርጎ የሚይዘው!? አሳማን ሊፒስቲክ መቀባት ይቻላል፣ ሆኖም ግን አሁንም ያው አሳማ ነው፡፡ እንደዚሁም ሁሉ ሁሉንም የአፍሪካ ዘራፊ አምባገነኖች የEITI አባል ማድረግ ይቻላል፣ እናም ግልጸኝነት እና ተጠያቂነት ብሎ መጥራት ይቻላል፡፡ በቀኑ መጫረሻም ያው አንድ ዓይነት ዩኒፎርም የተሰፋላቸው የዝርፊያ ቦርሳዎችን ይዘው የሚዞሩ ዘራፊ አምባገነኖች ናቸው፡፡

በኢትዮጵያ ውስጥ መሰቃየት፣ ኃይልን መጠቀም እና ጭካኔ ከጊዜ ወደ ጊዜ በመቀጠል ላይ ይገኛል፣

ማዳም ሾርት ለአንድ አፍታ እንዲህ በማለት አሰቡ፣ ”እኔ እንደማስበው መሰቃየቱ፣ በኃይል መጠቀም እና ጭካኔ የተሞላበት ሁኔታዎች በጓንታናሞ እስር ቤት እና በኢራቅ ላይ ቀጥለዋል፡፡“ ደህና፣ እንዲሁም ለኢትዮጵያ በተመሳሳይ መልኩ አስባለሁ፡፡ በኢትዮጵያ የሚደረገው ማሰቃየት፣ የኃይል እርምጃ እና ጭካኔ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየቀጠለ ነው፡፡ ጋዜጠኞች ይታሰራሉ፣ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ይዘጋሉ፣ የተቃዋሚ ፖለቲካ ድርጅት መሪዎች እንዲሸማቀቁ እና በፍርሀት ቆፈን እንዲጠመዱ እና እንዲታሰሩ ይደረጋሉ፣ ሰላማዊ አመጸኞች በኃይል እንዲጨፈለቁ ይደረጋሉ፣ እንዲሁም ምርጫዎች በጠራራ ጸሐይ ይጭበረበራሉ፡፡ ይህ ሁሉ ግን ሰላማዊ የሽግግር ለውጡን ሊያቆመው አይችልም፡፡ ያ ሁኔታ ይቀጥላል፣ ይቀጥላል… የኢትዮጵያ ወጣት ሴቶች እና ወንዶች ይነሳሉ እናም ለነጻነታቸው እንዲህ በማለት ይጮሃሉ፣

“ከዚህ በኋላ ትዕግስታችን ተሟጧል! ተርበናል! ነጻነት እንፈልጋለን! ነጻነት እንፈልጋለን! እስክንድር ይፈታ! አንዷለም ይፈታ! አቡባከር ይፈታ! ርዕዮት ትፈታ! የፖለቲካ እስረኞች በሙሉ ይፈቱ! ፍትህ እንፈልጋለን! ነጻነት! ነጻነት! ነጻነት! አትከፋፍሉን! ኢትዮጵያ አንድ ነች! አንድ ኢትዮጵያ! ከዚህ በኋላ ትዕግስታችን ተሟጧል! ውኃ ናፈቀን! መብራት ናፈቀን! ተርበናል!…“

በጓንታናሞ እና በኢራቅ ውስጥ የሚካሄዱትን ስቃዮች፣ የኃይል እርምጃዎች እና ጭካኔዎች በሚመለከት ማዳም ሾርት የአሜሪካ ፕሬዚዳንቶችን ተጠያቂዎች እንዳደረጓቸው ሁሉ እኔ ደግሞ በኢትዮጵያ ውስጥ ያሉት የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች ጠቅላላ ከጠፉ በኋላ ማዳም ሾርትን ተጠያቂ አደርጋለሁ፡፡

ማዳም ክላሬ ሾርት፣ “ተከሰዋል…!”

“እውነትን በዘጉ ጊዜ እና ከመሬትውስጥበቀበሯትቁጥር ድርጊቱን ማድረግ ይቻላል፣ ሆኖም ግን እውነት እያደገች፣ እየጠነከረች ትሄዳለች፣ እናም በአንድ ላይ ተሰባስባ የሚፈነዳ ኃይል ትፍጥራለች፣ በምትፈነዳበት ዕለት ሁሉም ነገር እራሷ በቀየሰችው መንገድ ይፈነዳል፡፡“ ኢሚሌ ዞላ

ኢትዮጵያ በክብር ለዘላለም ትኑር!

↧

ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ቶማስ አረፉ

$
0
0

የቀድሞ ስማቸው አባ መዘምር ተገኝ የአሁኑ ብፁዕ አቡነ ቶማስ ጥር 14 ቀን 1932 ዓ.ም ጎጃም ደጋ ዳሞት ዝቋላ አርባዕቱ እንስሳ ተወለዱ፡፡ መሠረታዊ የቤተ ክርስቲያን ትምህርትን በሚገባ ከተማሩ በኋላ ጸዋትወ ዜማን ከመሪጌታ አንዱዓለምና መሪጌታ ካሣ ይልማ ፣ ቅኔ ከመሪጌታ ፈንቴ /ዋሸራ/፣ መጻሕፍተ ሐዲሳትን ከመሪጌታ ብርሃኑ ወልደ ሥላሴ ፣ መጻሕፍተ ሊቃውንትን ከመሪጌታ ቢረሳ ደስታ ተምረዋል፡፡ በዘመናዊ ትምህርትም እስከ 6ኛ ክፍል ፣ የእንግሊዝኛን ቋንቋ በግላቸው የተማሩና የመኪና ጽሕፈት /type writing/ የሚያውቁ ነበሩ፡፡ ብፁዕ አቡነ ቶማስ ዲቁና ከአቡነ ማርቆስ፣ ቅስና ከአቡነ ባስልዮስ፣ ቁምስና ከብፁዕ አቡነ ተክለሃይማኖት ተቀብለዋል፡፡
abuna tomas

በደብረ ሊባኖስ ገዳም መጻሕፍተ ሊቃውንትን ረዘም ላለ ጊዜ አስተምረዋል፡፡ በገዳሙ የሠራተኞች ቅርንጫፍ ማኅበር ሲቋቋምም የመጀመሪያው ሊቀ መንበር በመሆን አገልግለዋል፡፡ ከዚያም ወደ አዲስ አበባ ተዛውረው በጎፋ መካነ ሕያዋን ቅዱስ ገብርኤል ካቴድራል በአስተዳዳሪነትና መጻሕፍተ ሓዲሳትንና ሊቃውንትን በማስተማር የሚጠበቅባቸውን ተልእኮ ተወጥተዋል፡፡ ጥር 14 ቀን 1972 ዓ.ም በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ተክለሃይማኖት ፓትርያርክ ዘኢትዮጵያ አንብሮተ ዕድ ተሹመው ሰፊ አገልግሎት ሲሰጡ ቆይተዋል፡፡ ከዚያም ወደ አዲስ አበባ በመመለስ የታእካ ነገሥት በዓታ ለማርያምና መንበረ መንግሥት ግቢ ገብርኤል ገዳም የበላይ ጠባቂ ሆነው አገልግለዋል፡፡
abuna tomas 2
ብፁዕነታቸው ከ2004 ዓ.ም ጀምሮ የምእራብ ጎጃም ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በመሆን ሲያገለግሉ ቆይተው፤ ባደረባቸው ሕመም በሕክምና ሲረዱ ቆይተው መጋቢት 16 ቀን 2006 ዓ.ም መንበረ ጵጵስናቸው በሚገኝበት በፍኖተ ሠላም ከተማ ዐርፈዋል፡፡ ሥርዓተ ቀብራቸውም በዚያው በፍኖተ ሰላም እንደሚፈጸም ይጠበቃል፡፡

ምንጭ፡ ማህበረ ቅዱሳን

↧

ለአማራ ወያኔዎች የመጀመሪያና የመጨረሻ መልእክት

$
0
0

 ነፃነት ዘለቀ (ከአዲስ አበባ)

“መልእክት” ያልኩት አቀራረቤን ቀለል በማድረግ የአንባቢያንን ቀልብ ላለመግፈፍ ነው፡፡ እንጂ መነሻየ ጥብቅ ማስጠንቀቂያ ለመስጠት ነው፡፡ ማስጠንቀቂያም ይባል መልእክት ዋናው ጉዳይ በግሌ የተሰማኝንና የማምንበትን ለወገኖቼ ድኅነት ስልም የምጽፈው ነገር ለባለአድራሻዎቹ መድረሱ ነው፡፡ ለዚህ ደግሞ የሁሉንም ድረገጾች ትብብር በአክብሮት እጠይቃለሁ፡፡ እባካችሁን ለሁሉም ካድሬ መልእክቴን አድርሱልኝ፡፡

ሰው ክርስቶስን መሆን እንዳይችል ጠላት መንገድ እየዘጋበት መቸገሩ የሚታወቅ ነው፡፡ መሆን  ቢፈልግ ግን ይችላል፤ የሚከለክለው አንዳችም ነገር የለም፡፡ ክርስቶስ ራሱም ያለው “እንደኔ ሁኑ፤ እኔን ምሰሉ” ነው፡፡ ችግሩ ክርስቶስን ለመሆን ወይም ቢያንስ ለመምሰል የእምነት ጽናትና እውነተኛ ፍቅርን የተላበሰ ስብዕና ማጣት ነው፡፡ ተራራን ሊያዞር የሚችል እምነት፣ የሚጠላንን ብቻም ሳይሆን የሚገድለንንም ጭምር  የሚያፈቅርና ለጨካኞች የሚራራ ልብ፣ የማይወላውል እምነትንና የማያዳላ ፍቅርን የሚገልጥ በጎ ሥራ ካለ ከፈጣሪና ከአንድያ ልጁ ከኢየሱስ ክርስቶስ ጋር ውህደት መፍጠርና ጓደኛ መሆን የማይቻልበት ምክንያት የለም፡፡ የሚጠይቀው እውነተኛ የልብ መሰበርን ብቻ ነው፡፡

ክርስቶሳዊ ተምሳሌትነትን በተወሰነ ደረጃ በመውሰድ አካሄድን ማረቅና ማስተካከል ይቻላል፡፡ ከወቅቱ አቢይ ሃይማኖታዊ ክንውን እንጀምር፤ ኢየሱስ ክርስቶስ አርባ ቀንና አርባ ሌሊት ከፆመ በኋላ በሰይጣን ሦስት ጥያቄዎች ቀርበውለት በአሸናፊነት ተወጥቷል፡፡ የመጀመሪያው ጥያቄ እንዲህ የሚል ነበር፤ “አንተ የእግዚአብሔር ልጅ ከሆንክ እስኪ እነዚህ ድንጋዮች እንጀራ እንዲሆኑ እዘዝ”፡፡ የክርስቶስም መልስ “ ‹ሰው የሚኖረው እግዚአብሔር በሚናገረው ቃል እንጂ በእንጀራ ብቻ አይደለም› ተብሎ ተጽፏል፡፡” አዎ፣ ለአስተዋይ ሰው በእንጀራ ብቻ መኖር እንደማይቻል ግልጽ ነው፡፡ እርግጥ ነው ሰይጣን በሚያስፈልገን ነገር ይመጣብናል፡፡ ሰይጣንና የስለላ ድርጅቶች ተመሳሳይነት አላቸው፤ በምትወደው ነገር ይመጡብህና ወጥመዳቸው ውስጥ ይከቱሃል(cf. blackmailing)፡፡ ክርስቶስንም በዚያ ቀዳዳ የመጣበት አርባ ቀንና አርባ ሌሊትን ካለምንም ምግብ በመክረሙ ተርቦ ነበርና ይሸነፍልኛል ብሎ ነው፡፡ እንዳሰበው ግን አልሆነለትም፡፡ ያ ምናልባት ሥነ መለኮታዊ ጣጣ ስላለው ለምድራዊ ሕይወት ጥሩ አብነት ላይሆን ይችላል፡፡ እናም የአርባ ቀኑን የክርስቶስ ፆም እንርሳውና አብዛኛው የአሁኑ ዘመን ሰው አንድ የምግብ ሰዓት አልፎበት አይደለም ትንሽ ሆዱ ጎደል ካለ እናቱን ከመሸጥ እንደማይመለስ እናስብ፡፡ አሰብን?…

ፈተናዎች በጥቅሉ የሥጋና የነፍስ ተብለው በሁለት ዐቢይ ክፍሎች ሊመደቡ ይችላሉ፡፡ በአማርኛ ፈተናን የሚገልጡ ቃላት ውሱን ናቸው፡፡ በዚህ ረገድ እንግሊዝኛው ሳይሻል አይቀርም፡፡ “test, quiz, exam, examination, temptation, assessment …” የሚባሉ ቃላት አሏቸው፡፡ እነዚህ ቃላት በዐውድ ውስጥ መገኘት ሳያስፈልጋቸው በቁማቸው የሚሰጡት የተወሰነ ምስል አለ፡፡ እኔ አሁን እዚህ ላይ ልጠቅሰው የምፈልገው የፈተና ዓይነት በእንግሊዝኛው አጠራር temptation የሚለውን ነው፡፡ የአባታችን ሆይ ጸሎት ውስጥ “ Our Father who art in heaven … lead us not into temptation but deliver us from evil.” እንደሚል፡፡

ከመጽሐፍ ቅዱስ ሳንወጣ የክርስቶስን ደቀ መዝሙርና የግምጃ ቤት ኃላፊ የአስቆሮቱ ይሁዳን እናስታውስ፡፡ ከገቢ ገንዘቦች አሥር መቶኛውን ለራሱ እንዲያደርግ ተፈቅዶለት የነበረው ይሁዳ በገንዘብ ፍቅር ክፉኛ የተለከፈ ነበር – ልክ እንደወያኔ፡፡ ይህ በሽታው ተባብሶበት በመጨረሻው ክርስቶስን ራሱን በሠላሣ አላድ ለጠላቶቹ አሳልፎ ሸጦታል፡፡ ገንዘቡን ግን አልተጠቀመበትም፡፡ ያልተጠቀመበትም ምክንያት ክፍያውን እንደተቀበለና ክርስቶስን ያሳድዱት በነበሩ አይሁዳውያን እንዳስያዘው የሰረፀበት ሰይጣን ለጸጸት አጋልጦት በመለየቱ ምክንያት ራሱን ሰቅሎ ስለሞተ ነው፡፡ የይሁዳ ነፍስ አልተማረችም፡፡ ይህን እውነት ከመጽሐፍ ቅዱስ እናገኘዋለን – ሊማር አለመቻሉንም ጭምር፡፡

ሰው በተለያዩ ምክንያቶች ወደፈተና ይገባል፡፡ ለሆዱና ስለሆዱ በሆዱ የሚፈተን አለ፤ በሆድ መፈተን መጥፎ ፈተና ነው፡፡ ሀገርን የሚያሸጥ የሆድ ፍቅር የተጠናወተው ሰው ደግሞ በሕይወት ዘመኑ በሚኖረው የስብዕና መመሰቃቀል ብቻም ሣይሆን ልጆችን ወልዶ ቢያልፍ በሀፍረት አንገታቸውን ይደፋሉ፤ በሕዝብ ዘንድም መጠቋቆሚያ ይሆናሉ፡፡ታሪኩ የጠቆረና የትውልድ ማፈሪያ ይሆናል – አሁንም እንደወያኔ፡፡

አንድ ሰው ፈተናን ወደቀ የምንለው ነባር እምነቱንና ታማኝነቱን ለሆነ ጥቅም ሲል ክዶ ከትክክለኛው መንገድ ሲወጣ ነው፡፡ በዚህ ረገድ የኢትዮጵያን ወቅታዊ ታሪክ ስንመለከት ሁለት በፈተና የወደቁ አካላትን እናገኛለን፡፡

ዋናው ተፈታኝና ፈተናውን ከመነሻው የወደቀው ከትግሬው ብሔር የወጣውና ሕወሃት በመባል የሚታወቀው ፀረ-ኢትዮጵያና ፀረ-ሕዝብ ኃይል ነው፡፡ ለዚህ ድርጅት በፈተና መውደቅ መንስኤው ዓላማና ለጥቅም ነው፡፡ የሚታወቅን ነገር መዘርዘር አስፈላጊ አይመስለኝም፡፡

ሁለተኞቹ ተፈታኞች ሁሉን ነገር እያወቁ ለፍርፋሪ እንጀራና ለማያዙበት የይስሙላ ሥልጣን ሲሉ በሕወሃት ሥር በባርነት አድረው የወጡበትን ሕዝብ ለወያኔ የሸጡ ይሁዳ አማሮች – ብአዴን ተብዬዎቹ – ናቸው፡፡ በሃይማኖታዊ አገላለጽ ሕወሃትን ልምጭ አስይዘውና በሁለንተናዊ ዘመናዊ መረጃ ደግፈው ጃዝ ብለው የላኩት የታላቁ ወንድም (The Big Brother) ባለሟሎችን የሉሲፈር ደቀ መዛሙርት ልንላቸው እንችላለን፡፡ ታሪካዊ ቂም በቀል አርግዘው ኢትዮጵያን ለማጥፋትና በእግረ መንገድም ቤት ያፈራውን ሥልጣንና ሀብት በግል ለመቆጣጠር የተነሡ የትግሬ ወያኔዎችን  በሉሲፈር አጣማጅ በሰይጣን በራሱ ልንመስላቸው እንችላለን፡፡ ለሆዳቸው ያደሩ በተለይም የዕልቂት ዐዋጅ ከታወጀበት የአማራው ሕዝብ እንደተገኙ የሚነገርላቸው ከሃዲዎችን ደግሞ በሰይጣን አገልጋይነት ልንፈርጃቸው እንችላለን፡፡ የሆነው ሆኖ ትግሬም ይሁን አማራ ወይም ሌላ ከእውነተኛው የጤናማ ኅሊና መንገድ ወጥተው ኢትዮጵያን ለማውደም እስከተሰለፉ ድረስ ሁሉም የጥፋት ወኪሎችና የክፉ መንፈስ ምርኮኞች ናቸው፡፡

በኢትዮጵያ ያለው አጥፊ ኃይል ደግሞ የዓለም አቀፉ የጥፋት ኃይል ቅርንጫፍ ነው፡፡ ይህ በከፍተኛ ጥንቃቄና የሸር ጥልፍልፍ ወይም ሤራ (Conspiracy) የሚካሄድ የዓለምን ፖለቲካና ኢኮኖሚ የመቆጣጠር ዕቅድ ጅማሮው ቀደም ቢልም በሁሉም አቅጣጫ በተቀነባበረ ዘመቻ ወደስኬት ጫፍ የደረሱ የመሰሉት ግና አሁን በምንገኝበት የ21ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ነው – የመሠረት ግንባታው ደርዝ መያዝ የጀመረው ግን የዛሬ 300 ዓመታት አካባቢ በ18ኛው መ/ክ/ዘመን መግቢያ አካባቢ እንደሆነ ይነገራል፡፡ የሚያሠማሯቸው ጉዳይ አስፈጻሚ ተላላኪዎች ዘርና ቀለም፣ ፆታና ሃይማኖት ሳይገድባቸው እንደ እስስት ከየሚሄዱበት አካባቢ ሕዝብ ጋር እየተመሳሰሉ ሀገርንና ሕዝብን በቅርበት ይቆጣጠራሉ – ሲያሻቸው መጽሐፍ ቅዱስ ሲያሻቸው ደግሞ ሽጉጥ በመያዝ በመስቀል ከቀላጤ ‘politico-psuedo-religious’ ዘመቻ ዓላማቸውን ከግብ ለማድረስና የባሕርይ አባታቸውን ሊቀ ትጉሃን ዲያብሎስን ለማስደሰት ይጥራሉ፡፡ በመንግሥታት ጀርባ ሥውር መንግሥታትን በማቋቋም ሁሉንም ነገር በዐይነ ቁራኛ ይከታተላሉ – ሊያውም በ“ሁሉን ተመልካች” አንዲት ዐይናቸው! በዓለም አቀፍ ግዙፍ ካምፓኒዎቻቸው አማካይነትም የዓለምን ሀብትና ንብረት ይዘርፋሉ፤ ነዳጅና የተፈጥሮ ማዕድናትን እያሰሱ ለማይጠረቁት ሥውር ቱጃሮቻቸውና የምሥጢራውያን ድርጅቶቻቸው አለቆች ያስረክባሉ – ሁሉ በጃቸው ሁሉ በደጃቸው፤ ጦሩም ስለላውም አስተዳደሩም ምኑም ምናምኑም በነሱው ቁጥጥር ስለሚገኝ የ‹ሪሶርስ›ና የሰው ኃይል ችግር የለባቸውም፡፡ ጦርነቶችን ይፈጥራሉ፤ ሲፈልጉ ያጣላሉ – ሳይፈልጉ ያስታርቃሉ፡፡ መሣሪያዎቻቸውን ለተዋጊ ወገኖች በግልጥና በድብቅ ይሸጣሉ፡፡ ትውልድን ከሃይማኖትና ከባህል አውጥተው መና ለማስቀረት፣ ከሞራልና ሥነ ምግባር ማዕቀፎች ለይተው ባዶ ለማስቀረት እነሆሊውድን ከመሳሰሉ ተቋሞቻቸው ባፎሜታዊ ፊልሞችንና ሙዚቃዎችን በዓለም ይበትናሉ፡፡ ሀሺሺንና መጠጦችን በማምረት በሥውር ያሰራጫሉ፡፡ የሚገርመው እነዚህ ኃይሎች ፀረ-ሀሽሽ መስለው ቢቀርቡም ውሸታቸውን ነው፤ ከአፍጋስታን እስከ ኮሎምቢያና ሜክሲኮ የዐደንዛዥ ዕፅ ምርትና ገበያን የተቆጣጠሩት እነሱው መሆናቸውን የሚገልጡ መረጃዎች የአደባባይ ምሥጢር ከሆኑ ሰንብተዋል፡፡ ወያኔም እንደዚሁ ወጣቱን በጫትና በመጠጥ እያደነዘዘ ሀገር ተረካቢ ትውልድ እንዳይኖር መጣሩን አንርሳ፡፡ በብዙ ነገር መመሳሰላቸውን ልብ እንበል፡፡ ወያኔን የሚገዛ ህግ እንደሌለ ሁሉ እነሱንም የሚገዛ ህግ የለም፡፡ የነሱን ደንቆሮ በሀሰት የዶክትሬት ዲግሪ የምስክር ወረቀት ለዓለም አቀፍ ተልእኮ ቢያሰማሩት ታማኝነቱ እንጂ ትምህርቱ ብዙም ፋይዳ ስለሌለው በአጭበርባሪነት የሚጠይቀው የለም – በወያኔ ቤትም ለባለሥልጣን ያልተበተነ የዲግሪ ዓይነት የለም – ባዶ ጭንቅላት ላይ ጥቁር ቆብና ጥቁር ካባ፡፡ ከነሱ ቁጥጥር የሚወጣን ሀገር መሪ(ዎች) በስለላ ድርጅቶቻቸው ልዩ ኮማንዶና በጨረር አነጣጥሮ ተኳሽ የፓራትሩፐር እስኳድ ያስወግዳሉ – ለሀገሩ የሚቆምን ሀገር ወዳድ ግለሰብም በዚህ መልክ ደመ ከልብ ሆኖ እንዲቀር ያደርጋሉ (ነፍስ ይማር – ኢቅእ(?))፡፡ (ቅን ታዛዦቻቸው ሊያፈነግጡ ወይም ጌታ ሊለውጡ ካሰቡም ይሄው የቅጣት በትር አይቀርላቸውም (ነፍስ ይማር – መዜአ (?))፡፡ … በሚያስወግዷቸው ምትክም የነሱን ፍላጎትና ጥቅም የሚያስከብር መለስ ዜናዊን የመሰለ ፀረ-ሕዝብና ፀረ-ሀገር ወሮበላ በዴሞክራሲ ጭምብላቸው ለላንቲካው ይጎልቱታል – ዋናውን መዘውር በእጅ አዙር የሚይዙት ግን እነሱው ናቸው፡፡ በዓለም ባንክና በአይ ኤም ኤፍ፣ በኔቶና በተባበሩት መንግሥታት የፀጥታው ምክር ቤት አማካይነትም በማይወዱት ሀገር ላይ የኢኮኖሚና ወታደራዊ ማዕቀብ ይጥላሉ፤ እንዳስፈላጊነቱም ጦርነት ያውጃሉ፡፡ ከነሱ ዕይታና ቁጥጥር ውጪ የሚሆን አንዳችም ነገር የለም፡፡ ነፍስና ሥጋህን ብቻ ሳይሆን የምታስበውንም ሁሉ ጭምር በ“Mind Control system”  ሊቆጣጠሩ ይሞክራሉ፡፡ ከፈለጉም በሰው ሠራሽ የመሬት መናወጥና ሱናሚ አንድን ሀገር ሊያደባዩ፣ አለዚያም በዘመናዊ የቴክኖሎጂ መራጃ ዝናብን ከልክለው በድርቅ ሊመቱ፣ በሌላም በኩል ከመጠን በላይ ዝናብን አዝንበው በጎርፍና በመሬት መንሸራተት ናዳ ሕዝብንና መንግሥታትን ሊያስለቅሱ ይችላሉ፡፡ በአጭሩ የማያደርጉት ነገር የለም፡፡ ደግሞም እውነት ነው፡፡ ወያኔዎችስ? ሥልቱና አፈጻጸሙ ይለያይ እንጂ አንድና አንድ ናቸው፡፡

የወያኔዎች የአንድ ለአምስት የጥርነፋ ሥልት የዚሁ የዓለም አቀፍ ዘመቻ አካል ነው፡፡ በአነስተኛ ብድርና ቁጠባ ዕዳ ውስጥ የሚዶሉህም በዐይናቸው ሥር አውለው ሊቆጣጠሩህ ነው፡፡ በብድር የተያዘ ሰው ደግሞ ታውቃለህ – ውልፊት ሊል አይችልም፡፡ ሌላ ነገር አምሮህ ብታንጋጥጥ- ማንጋጠጥም አይደለም ለማሰብም ብታስብ ራሱ ያስወነጅልሃል፡፡ ያኔ በአሸባሪነት ባትጠየቅ እንኳን በገንዘብ ዕዳ ያለህን ንብረት ያሸጡሃል ወይም የፍትሃ ብሄር ወንጀልህ ተቀባብቶ ወደ ተሟላ ደረቅ ወንጀል ይዞርብህና ቃሊቲ ልትወርድ ትችላለህ፤ ለማንኛውም እሥር ቤት ውስጥ ነህ – የእሥር ቤቱ ስፋትና ጥበት ላይ የጋራ መግባባት ላይ እስከደረስን ድረስ፡፡ በቤትህ ውስጥ ሳይቀር ከአንተ ዕውቀት ውጪ ተከታታይ ሊመደብብህና መላ እስትንፋስህ ወደ ማዕከላዊ መረጃና ደህንነት መሥሪያ ቤት ሊያመራ ይችላል፤ ስልክህ ሊጠለፍ፣ ኢሜልህ ሊጠለፍ፣ ፌስቡክህ ሊጠለፍ፣ ሚስትህ ልትጠለፍ፣ ልጆችህና ጓደኞችህ ጭምር ሊጠለፉ፣ አስፈላጊ ሆኖ በተገኘ ጊዜ ሁሉ አንተ ራስህም ልትጠለፍና የሰይጣን ጆሮ ይደፈንና ብዙ ሰይጣናዊ ነገሮች ሊደርሱብህ ይችላሉ፡፡ የእነአልማዝ ሠይፉን፣ የእነብርቱካን ሚዴቅሳን፣ የእነደበበ እሸቱን፣ የነስዬ አብርሃን ዝምታ ያዬ አንዳች ነገር ቢጠረጥር ሊፈረድበት አይገባም፡፡ በስማም የተባለበት ሰይጣን ይመስል በአርምሞ የተቀመጡበትን ምክንያት ከነሱ በስተቀር ማንም አያውቅም፡፡ አሣሪህና የስቃይህ ምንጭ ሲደርቅ ጮቤ መርገጡ ዲያብሎሳዊ መሆኑ እርግጥ ቢሆንም ለሰባት ቀን ሀዘን መቀመጡና በፈጣሪ ሥራ ገብቶ በ“ለምን ወሰድክብኝ” እዬዬ ማለቱ ሃይማኖታዊ መደላድል ያለው አይመስለኝም – የቃል መቀነት መጠቀም አስፈላጊ ሆኖ የተገኘውም ይህን ዕንቆቅልሽ በአመስጥሮ ለመጠቆም ነው (አመስጥሮው እዚህ ላይ አበቃ እንጂ)፡፡ ለማንኛውም በዲያብሎስ ግዛት መብቴ ተረገጠ ሰው መሆኔ ተዘነጋ ብሎ መጠየቅ ሞኝነት ነው፡፡ ከሁሉ በባሰ ሁኔታ የጎንህ ፍላጭ ሚስትህ ወይም የአብራክህ ክፋይ ልጅህ ሊሰልሉህ ቢችሉ የዘመኑ የትልቁ ወንድምህ ፋሽን ነውና አይግረምህ፡፡ ወያኔ የትልቁ ዓለም አቀፍ ዘመቻ የምሥራቅ አፍሪካ ዋና መሥሪያ ቤት (Head Quarter) ነው ቢባል ያስኬዳል፡፡ ከጆርጅ ኦርዌል ድንቅ መጽሐፍ (ከ “1984” ውስጥ) እስኪ ቀጣዩን ጥቅስ እንመልከት፡፡

 

He [Winston Smith] took a twenty-five cent piece out of his pocket. There, too, in tiny clear lettering, the same slogans were inscribed, and on the other face of the coin the head of Big Brother. Even from the coin the eyes pursued you. On coins, on stamps, on the covers of books, on banners, on posters, and on the wrappings of a cigarette packet—everywhere. Always the eyes watching you and the voice enveloping you. Asleep or awake, working or eating, indoors or out of doors, in the bath or in bed—no escape. Nothing was your own except the few cubic centimetres inside your skull.

 

ተዛማጅ ትርጉም፡- (ዊንስተን ስሚዝ) ሃያ አምስት ሳንቲም ከኪሱ አወጣ፡፡ በዚያች ሣንቲም ላይም በአንደኛው ገጽ በጥቃቅን ፊደላት የተለመደው መፈክር ተጽፏል፤ በሌላኛው ገጽ ላይ ደግሞ የታላቁ ወንድም የራስ ምስል ጉብ ብሏል፡፡ [(መፈክሩ - ‹ ጦርነት ሰላም ነው፤ ነጻነት ባርነት ነው፤ ድንቁርና ጥንካሬ ነው፡፡› የሚል ነው1፡፡)] ከዚህች ትንሽዬ ሣንቲም የምታየው የታላቁ ወንድም ዐይኖች ትክ ብለው ሲያዩህ መግቢያ ያሳጡሃል፡፡ በሣንቲሞች፣ በቴምብሮች፣ በመጽሐፍ ሽፋኖች፣ በዓርማዎች፣ በፖስተሮች፣ በሲጋራ ወረቀቶች፣ የትም ይሁን የትም እነዚህ የታላቁ ወንድም ዐይኖች ያፈጡብሃል፡፡ ምን ጊዜም ዐይኖቹ መግቢያ መውጫህን ይከታተላሉ፤ ድምፆቹም የጆሮ ታምቡርህን ያለ ዕረፍት ይጠልዛሉ፡፡ ተኝተህም ሆነ ሳትተኛ፣ ሥራ ላይም ሆንክ ምግብ ላይ፣ ከቤት ውስጥም ሆንክ ከቤት ውጪ፣ መታጠቢያ ቤትም ውስጥ ሁን በአልጋህ ላይ … የትም ሁን የት ከታላቁ ወንድም ዐይኖችና የዘወትር ክትትል ማምለጫ የለህም፡፡ ጭንቅላትህ ውስጥ ከሚገኘው ነጭ አንጎል ውጪ የኔ ነው የምትለው የግል ንብረት እንዲኖርህ አይፈቀድልህም፡፡ [እርሱንም ቢሆን አንተ አታዝበትም!]

 

በዲያብሎስ መንፈስ የሚነዳውን የአፍራሽ ኃይል (The Negative Energy) ዓለማቀፋዊ የጥፋት አድማስ በአጭሩ ለማሳየት የሞከርኩት የሀገራችን ጉዳይም ከዚሁ ኃይል ጋር ቀጥተኛ ቁርኝት ያለው በመሆኑ ነው፡፡ ከዘመን ፍርድ ማምለጥ አስቸጋሪ ነውና፡፡ ዓለማችን የሁለት ተፃራሪ ኃይላት መስተጋብራዊ ውጤት ናት፤ እነሱም ገምቢ ወይም አወንታዊ ኃይልና አፍራሽ ወይም አጥፊ ኃይል ናቸው፡፡ ማንም ሰው ከነዚህ ሁለት እርስ በርስ ተጠፋፊ ነባራዊ ሁኔታዎች ውጪ አይደለም፡፡ በምንገኝበት መሬታዊ/ምድራዊ ተጨባጭ ሁኔታ መሠረት አንዱ ካለ ሌላው አይኖሩም፡፡ ገምቢ ካለ አፍራሽ አለ፡፡ በዬቋንቋዎቻችንም ደግ – ክፉ፣ ፍቅር – ጥላቻ፣ ቸር – ንፉግ፣ ሃቀኛ – ዋሾ፣ ወዘተ. የመኖራቸው እውነታ ይህንን ለማጠየቅ ይመስላል፡፡ ችግሩ ምጣኔያቸው ላይ የሚታየው የሚዛን መዛነፍ ነው፡፡ አንዱ ከሌላው ግዘፍ ነስቶ ከታዬ ለምሳሌ የክፋት መንፈስ ከተንሠራፋ ሀገርና ሕዝብ ይጎዳሉ፤ እንደሀገረ ኢትዮጵያ ለአጠቃላይ ውድመት ሊዳረጉም ይችላሉ፡፡ ይህ ዓይነት አስቀያሚ ሁኔታ የሚፈጠረው ኅሊናን በመሸጥ ለሆድና ለጥቅም ማደር ሲከሰት ነው፡፡ ሰዎች ኑሯቸውን ያሸነፉና ያለፈላቸው እየመሰላቸው ብዙ ጣጣ ውስጥ ይገባሉ፤ በዚያም ሳቢያ ከፍለው የማይጨርሱት ዕዳ ውስጥ ይነከራሉ፡፡ የብአዴኖች ወንድምና እህቶቻችን ዕኩይ ተግባርም ከዚህ የሚመደብ ነው – በደቂቃዎች ውስጥ ዕዳሪና ሽንት ለሚሆን የሆድ ቀለብ (እህልና ውኃ)  ሀገርንና ሕዝብን የመሰሉ ዘላለማውያን ኅላዌያት ሲክዱ ማየት የታሪክ አሰቃቂ ፍርድና ምፀት ነው፡፡

ሕወሃት ኢትዮጵያን እያጠፋ ያለው ለዓላማና ለጥቅም ነው፡፡ የሕወሃት ተባባሪዎች የሆኑት ብአዴንና ሌሎቹ ኢትዮጵያን በማጥፋት ላይ ከሚገኘው ሕወሃት ጋር እየተባበሩ ያሉት ወገኖች ግን ለዓላማ ሣይሆን አንድም በድንቁርና ነው፤ አንድም በሆዳምነት ነው፡፡ አማራ አማራን ከምድረ ገጽ ለማጥፋት ዓላማ ነድፎ ከፀረ-አማራ ኃይሎች ጋር በማበር ሊንቀሳቀስ ይችላል ተብሎ መቼም አይጠበቅም፤ በውነቱ የብአዴኖችን ነገር ስናጤነው የእርግማን ካልሆነ የሌላ አይመስልም፤ ዕንቆቅልሽ ነው፡፡ ምክንያቱም አንድ አማራ ካልታመመ በስተቀር ዘመዶቹን ለመፍጀት በፖለቲካ ፕሮግራሙ ላይ ሳይቀር በመታገያ ዓላማና ግብነት ቀርፆ የሚንቀሳቀስን ሰይጣናዊ ኃይል ሊተባበር አይችልምና ነው፤ በምንም ዓይነት መንገድ፡፡ ተጠየቃዊ አካሄዱም ይህን ታሪካዊ ህፀፅ ሊዳኝበት የሚያስቸለው ክፍተት የለውም – “ዕብደት ነው!” ብሎ የሚያልፈው ካልሆነ በስተቀር፡፡ በመሆኑም ብአዴን ውስጥ የሚገኙ አማሮች በየትኛውም ሚዛን ቢለኩ አንድም የለየላቸው ዕብዶች ወይም የለየላቸው ደናቁርት ማይማን ወይም ደግሞ ፀላኤ ሠናያት የሠፈረባቸው የክፉ መናፍስት ዋሻዎች ቢሆኑ እንጂ ለአማራ የሚቆረቆሩ አማሮች ሊሆኑ አይችሉም – ቃል ቢቸግረኝ እንጂ “ማይም” ማለቴ ራሱ ስህተት ነው፡፡ ማይምነት ከሀገር መሸጥና መለወጥ አይገናኝምና፡፡ ብአዴኖች አማራ አይደሉም ሲባል ደግሞ የደምና የአጥንት ጉዳይ ሳይሆን በፍካሬያዊ ትርጉሙ ነው፡፡ አማራን ከሚያጠፋ፣ ኢትዮጵያን ለመቅበር ጉድጓድ ከማሰ፣ ሀገርን ከሸጠና ከለወጠ ኃይል ጋር ያለ ሀፍረት አብሮ እየሠራ የሚገኝ “ሰው” አማራ ነኝ ቢል እንዴት ማመን እንደሚቻል ብአዴኖችን ራሳቸውን መጠየቅ ነው፡፡ በጣሊያን ጊዜ ከቅኝ ገዢው ባዕድ ወገን ጋር በባንዳነት ያገለግሉ የነበሩ ብዙዎቹ የዛሬዎቹ ገዢዎቻችን ወላጆች በንጽጽር ከብአዴኖች ይሻላሉ፡፡ ምክንያቱም የዚያኔዎቹ ባንዳዎች የካዱት መላዋን ኢትዮጵያን እንጂ የወጡበትን ጎሣና ነገድ አልነበረምና፤ በዚያ ላይ ጣሊያንም ቢሆን የወያኔን ያህል ቀርቶ ካልነኩት የማይነካና በጭካኔው ከወያኔ ፍጹም የማይወዳደር በአንጻራዊ አነጋገር እጅግ ሲበዛ ሰብኣዊ የነበረ ኃይል ነው፡፡ የኒህኞቹ ድርጊት ግን ዘግናኝ ወንጀል ነው፡፡ ከዚህ አኳያ ወንድምህን፤እህትህን፤ አባትና እናትህን፣ በጥቅሉ በዘመኑ ቋንቋ ዘርህንና ቤተሰብህን እንደዐይጥ ከሚጨፈጭፍ የባንዳ ውላጅ ጋር መተባበር፣ ከዚያም ባለፈ ሰሞኑን እንደምንሰማው የጠላትን አንደበት በመዋስ በእንደራሴነትም ቢሆን የሚያስተዳድሩትን ሕዝብ በአደባባይ መዝለፍ በምንም ዓይነት መለኪያ ጤናማነትን አያሳይም፡፡ (Shall we say proxy badmouthing or insulting?) ይህ ዓይነቱ የብአዴን ድፍረት የኅሊና መታወርንና የአንጎል ጤንነት መቃወስን በግልጥ የሚያመለክት ነው፡፡ የአእምሮ ህክምናም ሳያስፈልገው አይቀርም፡፡…

አሁን ምን ማድረግ ይቻላል? በዚህ መቀጠሉ ያዋጣል ወይ? እስከመቼስ በባለ አንድ ጥርስ ማርሽ ብቻ ማሽከርከር ይቻላል?

ሰዎች ከፈለጉ ለማንኛውም ችግራቸው መፍትሔ መፈለግና ማግኘትም ይችላሉ፡፡ ዋናው ነገር ችግር ውስጥ መገኘትን ማወቅ ነው፡፡ ይህ በራሱ የመፍትሔውን ግማሽ መንገድ እንደመጓዝ ይቆጠራል፡፡ ከዚያም ንስሃ መግባት ነው፡፡ ንስሃ መግባት ሲባል በዚህ ዐውድ መሠረት በሆነ ታሪካዊ አጋጣሚ በተፈጠረ ስህተት ገብተው የሚዋኙበትን የጥፋት ባህር ተረድቶ ከዚያ ለመውጣት ከልብ መጸጸት ማለት ነው፡፡ ጥፋት ሰብኣዊ ነው፡፡ ማንም ሰው ትንሽም ይሁን ትልቅ ስህተት ይሠራል፡፡ ከስህተት ጎዳና ለመውጣትና ተበዳይን ከልብ ይቅርታ ጠይቆ ለመካስ የሚተጋን ሰው ደግሞ ፈጣሪ ይወደዋል፡፡ ሰው ሲባል ከሌሎች እንስሳት የሚለየውና ክፉንና ደግን መለየት የሚያስችለው አንጎል ያለው በመሆኑ ከስህተቱ እየተማረ፣ ደካማ ጎኑን እያስወገደና ጠንካራ ጎኑን ይበልጥ እያሻሻለ ወደበለጠ አእምሯዊና አካላዊ ዕድገት መራመድ ይጠበቅበታል፡፡ ጥፋቱን እንደልማት ቆጥሮ በኩራት የሚጀነን ሰው ከወያኔ የሚመደብ የመከነ አእምሮ ባለቤት ነው፡፡

መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ እንደምናነበው ብዙዎች ቅዱሳንና ሰማዕታት ስህተትን ይሠሩ ነበር፡፡ ከአዳምና ከሔዋን ጀምሮ እነቅዱስ ዳዊት፣ እነሶሎሞን፣ እነጴጥሮስ … ሁሉም ይሳሳቱ ነበር፡፡ ግና በጸጸት ዕንባቸው ስህተታቸውን እያጠቡ ከእግዚአብሔር ምሕረትን እንዳገኙ ቅዱሣት መጻሕፍቱ ያስረዳሉ፡፡ ክርስቶስንና ክርስቶሳውያንን በጦር ያሳድድ የነበረው ኃጢኣተኛው ሳዖል፣ በኋላ ላይ በደገኛው የኢየሱስ መንፈስ ተመርቶ አንገቱን ለሠይፍ እስኪሰጥ ድረስ የክርስቶስ አገልጋይ ሊሆንና በቅዱስ ጳውሎስነቱ ሊታወቅ በቅቷል፡፡ አንድ ነገር እንድገም፡- አንዱ “ወንድሜ ሰባት ጊዜ ስህተትን ቢሠራብኝ ሰባት ጊዜ ሁሉ ይቅር ልለው ይገባኛልን?” ሲል ክርስቶስን ይጠይቀዋል፤ በርሱ ቤት ሰባት ብዙ ቁጥር መሆኑ ነው፡፡ ክርስቶስ ግን በሚገርም ሁኔታ “ሰባት ጊዜ ብቻ አይደለም፤ ሰባት ጊዜ ሰባም ቢሆን ይቅር በለው” ሲል ነው የመለሰለት፡፡ አራት መቶ ዘጠና ጊዜ ቆጥረህ ይቅር በል ለማለት አይደለም – ይቅር ባይነት ገደብ እንደሌለው ነው የዚያ አስተምህሮ ማዕከላዊ አንድምታ፡፡ ይህ ምሳሌ ሁለት መልእክት አለው፡፡ አንዱ ለበዳዮች – ሌላኛው ለተበዳዮች፡፡ በበዳይ ወገን በኩል ያየነው እንደሆነ “ብዙ በድያለሁና ይቅር ስለማልባል በጥፋት ጎዳና እንደተጓዝኩ ዕድሜየኝ ልፍጅ” ከማለት ያድናል፡፡ በተበዳይ ወገን በኩል ሆነን ያየነው እንደሆነ “ዕድሜ ልኩን ሲጫወትብኝ ኖሮ አሁን እንዲህ እንዲህ ያለ ነገር እንዳይደርስበት ስለፈራ ልታረቅህ ይለኛል፤ ደግሞስ ለስንት ጊዜ ያህል ከበደለኝ በኋላ ለምን ብዬ ነው ይቅርታውን የምቀበለው?” ከሚል ሰይጣናዊ ግብዝነት ይታደጋል፡፡ እናስ ምን እናድርግ?

ንስሃ ለመግባት ቅድመ ሁኔታ የለውም፡፡ አንድ ሰው ንስሃ መግባት የሚያስፈልገው ጥፋት በማጥፋቱ ነው እንጂ ባያጠፋማ ለምን? ለይቅርታ ደግሞ የጥፋት ደረጃ ማነስ ወይ መብዛት ለድርድር አይቀርብም፡፡ ዋናው ከልብ መጸጸትና ጥፋትን እርግፍ አድርጎ መተው ነው፡፡

በኢሳት እንደምንከታተለው ከብአዴኖች ምሥጢር እየሾለከ ወደተቃውሞው ጎራ እንደሚገባ ተነግሯል – ከኢሳት አንጻር የመረጃ ምንጭን የማጋለጥ ምሥጢሩ እስካሁን ባይገባኝም (ይህ ዓይነቱ ልበ ሙሉነት የመረጃ ምንጭን በማድረቅ ረገድ አሉታዊ ሚና እንደማይጫወት ባውቅ ደስ ባለኝ)፡፡ ለማንኛውም ይህ መልካም ጅምር ነው፡፡ በራሱ ግን በቂ አይደለም፡፡ በጣም ኢምንት ነው፡፡ ሙሤን ማስታወስ ይገባል፡፡ ሙሤ በፈርዖን መንግሥት ውስጥ ሆኖ ወገኖቹን ከሚጨፈጭፍ ኃይል ጋር – ሳያውቅ ነው – ይሠራ ነበር፡፡ ማንነቱን ከተረዳ በኋላ ግን 40 ሺህ እስራኤላውያንን ይዞ ከምድረ ግብጽ በመውጣት ሕዝቡን ከአስከፊ አገዛዝ ነጻ አውጥቷል፡፡ ብአዴኖችም ይህን ለማድረግ መረጃ ከመስጠት ባለፈ ብዙ ይጠበቅባቸዋል፡፡ በሰፊው የአማራ መሬት የአፓርታይድንና የፋሺዝምን ሥርዓት ሕዝባቸው ላይ መጫናቸውን ትተው ከነፃነት ታጋዮች ጋር በኅቡዕ ኅብረት መፍጠርና የነፃነትን ጊዜ ማፋጠን አለባቸው፡፡ እስካሁን የሠሩት ጥፋት ፊታቸው ላይ እየተደቀነ ሊረብሻቸው አይገባም፡፡ ያን በንስሃ ማጠብ የሚቻለው የሠሩትን ስህተት የሚክስ መልካም ሥራ ሢሰሩ ብቻ ነው፡፡ አንድ ሰው ንስሃ ሲገባ ያጠፋ የነበረውን ጥፋት ዳግመኛ ላለመሥራት ቃል የሚገባበትና የዚያን ተቃራኒ ደግ ሥራ ለመሥራት በዚያውም በደሉን ለማካካስ (atonement) ሌት ተቀን የሚተጋበት ዕድል ያገኛል፡፡ ንስሃ መግባት ሲጀመር ከሙስናና ከደም ማፍሰስ፣ ንጹሓንን በፖለቲካ ሰበብ ከማሰርና ከማንገላታት መቆጠብ ይገባል፡፡ በተመሳሳይ ቅኝት የሚጓዝ ሕይወት መጨረሻው አያምርም፡፡ ብአዴንም ሆነ ሌላው የወያኔ ተባባሪ እሚበላው ያው አንዲት እንጀራ ናት – ከዚያች አታልፍም፡፡ በተረፈ በቅንጦቱ ረገድ ቢጠጣ ዊስኪና ቢራ ነው፡፡ ቢተኛ ሞዝቮልድ አልጋ ላይ ነው፡፡  ይህ ደግሞ ይሰለቻል፤ በወንጀልና በኃጢኣት ወገንን ሸጦ በሚገኝ የደም ገንዘብ ተንፈላስሶ መኖር የሚቻለው ለተወሰነ ጊዜ ብቻ ነው፡፡ ሰው የሆነ ሰው በደም ደለል ውስጥ መንቦራጨቁ እየተከሰተለት ሲመጣ በሂደት አእምሮውን የሚያስጨንቅ ነገር ይገጥመዋል፡፡ ጭንቀትን ለመሸፈን ከጧት እስከማታ በመጠጥ ብርጭቆ ውስጥ ቢወተፉ ኅሊና ቀስ እያለ መንቃቱ አይቀርምና በሁለትዮሽ የዞረ ድምር – በመጥፎ ሥራና በመጠጥ – መሰቃየት ይከተላል፡፡ ያኔ የሚከሰተውን የኅሊና ጅራፍ ደግሞ የሚቋቋመው የለም፡፡ ስለዚህ ብአዴኖች ከገባችሁበት አረንቋ በአፋጣኝ እንድትወጡ ብታውቁትም ባታውቁትም በኅያው እግዚአብሔር ስም እማጸናችኋለሁ፡፡ ይህን የምላችሁ ለሕዝብ በማዘን ብቻ እንዳይመስላችሁ፡፡ የምትሠሩት መጥፎ ሥራ ከሚያመጣባችሁ የዕልቂት ማዕበል እንድትተርፉ በቅንነት ለእናንተም በማሰብ ጭምር ነው፡፡ ሰው ዓለሙን ሁሉ ቢገዛ ነፍሱን ግን ማትረፍ ካልተቻለው ምን ይጠቅመዋል? ይላል መጽሐፉ፡፡ የምሕረት በር ሳትዘጋ አሁኑኑ በንስሃ ታጠቡ፡፡ ሕዝባችሁ አምርሮ ጸልዮኣል፤ ጸሎቱም ተሰምቷል፡፡ እግዚአብሔር ይመስገንና የኢትዮጵያ ሕዝብ ጸሎት በእግዚአብሔር ፊት ክብርንና ሞጎስን አግኝቶ መልስ የሚሰጥበት ጊዜ ተቃርቧል፡፡ ምልክቶቹም ሁሉ እየታዩ ነው፡፡ አንዱን ልንገራችሁ – ያ ወጣት ብላቴና ረዳት አብራሪ – ምንም ነገር ሳይቸግረው – ከነአውሮፕላኑ ለምን ያን የመሰለ ታሪክ የሠራ ይመስላችኋል? አስቡት፤ አስቡበትም፡፡ በዚህ መልክ ጥሪው የሚተላለፍላቸውና የነፃነት ፍልሚያውን የሚቀላቀሉ ወጣቶች በሠልፍ እየተጠባበቁ ናቸው፡፡

አፄ ቴዎድሮስ በጣም ጨካኝ እንደነበሩ ይነገራል፤ ምናልባትም በሁኔታዎች አስገዳጅነት ወደዚያ ደረጃ ተገፍተውም ሊሆን ይችላል፡፡ እርሳቸውም ያን ጠባያቸውን እንደሚያውቁና ሕዝብን ለመቅጣት ከፈጣሪ እንደተላኩ ለሚቀርቧቸው ይናገሩ እንደነበር ተጽፏል፡፡ አንድ ወቅት መነኮሳትን ከያሉበት ይጠሩና በየተራ እያስገቡ “ለመሆኑ እግዚአብሔር አሁን ምን እየሠራ ነው?” ብለው ይጠይቃሉ፡፡ ሁሉም የመሰለውን ይመልሳል፡፡ እርሳቸውን ያስደሰተች መልስ ግን አንድ ኮሣሣና ለነፍሳቸው ያልሳሱ (ሞትን የናቁ ማለቴ ነው) መነኩሴ “እግዚአብሔር በአሁኑ ሰዓት ቁናውን እየሰፋ ነው!” ሲሉ የተናገሩት ነው፡፡ አዎ፣ እሳቸውም አመኑበት፡፡ የሠሩትን ጥፋት ስለሚያውቁ፣ በሠፈሩት ቁና መሠፈርም ደንብ መሆኑን ስለሚረዱ አንገታቸውን ነቅንቀው በአግራሞት ነበር ያን መልስ የተቀበሉትና ባህታዊውን አመስግነው ወደመጡበት በክብር የሸኙት፡፡ ሌሎችን በትዝብት ዐይናቸው መግረፋቸውን ማስታወስ ካስፈለገ ግን ይሄውና አስታወስኩ፡፡

ወያኔንና ግብረ አበሮቹን ለመቅጣት እግዚአብሔር ቁናውን ሠፍቶ ጨርሷል፡፡ ወያኔን ያሣወረው ትዕቢት መቃብር ካልከተተው የማይለቀው ሆኖ እንጂ የወያኔ ጉድጓድ ከተማሰ፣ ልጡም ከተራሰና የመግነዝ በፍታውም ከተዘጋጀ ቆይቷል፡፡ የሚቀረው ሥርዓተ ግንዘቱና ጉዞ ፍትሃቱ ብቻ ነው፡፡ ያም በቅርቡ ይከናወናል፡፡ ለመሆኑ አሁን ሀገሪቷን ማን እያስተዳደራት እንደሆነ በግልፅ የሚያውቅ አለ? እኔ ከፈጣ ውጪ በሰው ደረጃ ኢትዮጵያን የሚያስተዳድር ሰው አላውቅም፡፡ እርግጥ ነው የሆነ የወያኔ ቡድን መኖሩን አልክድም፤  ዋናው ግን በኪነ ጥበቡ እንደምንለው በዚያ ልዩ መለኮታዊ ኪነ ጥበብ ነው ውለን የምንገባው፡፡ ለማንኛውም መላው የኢትዮጵያ ጠላቶች ሂሳባቸውን የሚያወራርዱበትና በኢትዮጵያ ሰማይ ላይ ወያኔ የናኘው ማንኛቸውም የዘረኝነትና የጎሰኝነት አቧራ እንደጉም በንኖ የሚጠፋበት የነፃነት ዘመን ደጅ ላይ ቆሟል፡፡ ይህን ነፃነት ማንም ፈቅዶ አይሰጠንም፤ ማንምም ታግሎ አይነጥቀንም፡፡ የዕንባችን፣ የጸሎታችንና የመገፋታችን ውጤት፣ በወያኔዎች ደባ ለዓመታት የፈሰሰው ደማችን የሚያመጣልን መለኮታዊ ፀጋ እንጂ የሰው ስጦታ አይደለም፡፡ በየከተማው እንደሚያፋድሱት እነአባ መሸ በከንቱን የመሰሉ ሳይሆን በሩቅ ገዳማትና በሥውር ሥፍራዎች ቀን ከሌት ወደፈጣሪ የሚያለቅሱ አባቶችና እናቶች አሉን፡፡ ቢያንስ እነሱን አያሣፍራቸውምና መልሱን በቅርብ እንጠብቃለን፡፡ ኢትዮጵያችን ጥቂቶች በቁንጣን የሚሰቃዩባትና ሚሊዮኖች በጠኔ የሚረፈረፉባት ሀገር ሆና እንደማትቀር ቃል ኪዳን አለ፤ ሀገራችን የቃል ኪዳን ምድር ናት፡፡ እናም አይዞን!!!

ብአዴኖች ግን ወደ ኅሊናችሁ ተመለሱ፡፡ ይህ ጥሪየ ዘርን መሠረት ባያደርግብኝ ደስ ባለኝ፡፡ ነገር ግን ይበልጥ የሚያሣዝኑኝ እነሱ በመሆናቸው ነው ይህን የተለዬ ጥሪ እነሱ ላይ በማተኮር ማስተላለፍ የወደድኩት፡፡ ፈጣሪ መንሹን ሊጨብጥ – ገለባን ከምርቱ ሊለይ የማበራያ ዐውድማውን ለቅልቆ ጨርሷል፡፡ ልብ ያለው ልብ ይበል፤ ከያዘው አሼሼ ገዳሜና አሥረሽ ምቺውም ይመለስ፡፡ የዚህ ዳንኪራና ጮቤ ወጪ የሚሸፈነው ከምሥኪኑ ሕዝብ እየተመዘበረና በሙስና እየተዛቀ መሆኑ የማይካድ ነው፡፡ በዚህ የጥፋት መንገድ እየነጎዳችሁ ያላችሁ ወገኖችም ለቁሣዊ ፍላጎቶቻችሁና ለሰይጣናዊ ሱሶቻችሁ ልጓም አብጁላቸው፡፡ ይህን ስል ወንድም በወንድሙ ላይ የሚፈጽመውን ግፍና በደል ያቁም፣ ወደኅሊናውም ተመልሶ ለሁሉም እኩል በሆነ ህግ ይተዳደር ለማለት እንጂ ሃይማኖታዊ ንስሃ ግቡና ፁሙ ቁረቡ ለማለት ፈልጌ አይደለም፡፡ ለዚያ ዓይነቱ ስብከት ይህ መድረክ ምቹ እንዳልሆነ አውቃለሁ፡፡ ሰላም ክረሙልኝ፡፡

 

መሰነባበቻ፡-

To the future or to the past, to a time when thought is free, when men are different from one another and do not live alone—to a time when truth exists and what is done cannot be undone: From the age of uniformity, from the age of solitude, from the age of Big Brother, from the age of doublethink—greetings!

 

ውርስ ትርጉም፡- ይድረስ የማላይህ የወደፊቱ ወይም ያልኖርኩብህ የኋለኛው ዘመን ትውልድ – በነፃነት ማሰብ ላልተከለከልከው፣ ሰብኣዊ ልዩነቶችህን ተረድተህ በሰላምና በፍቅር ተግባብተህ መኖር ለቻልከው፣ አምነህበት የምትሠራውን የሚያጨናግፍብህ ሳይኖር በእውነትና ስለእውነት መኖር ለበቃሃው ዕድለኛ ትውልድ ሰላምታየ ከዚህ ከተመሳስሎ የመኖር ዘመን፣ ከዚህ የብቸኝነት መንፈስ ሰውን ከሚያሰቃይበት የብህትውና ዘመን፣ ከዚህ ከታላቅ ወንድም የሰቆቃ ዘመን፣ ከዚህ ከአድርባይነትና አስመሳይነት ዘመን ባለህበት ይድረስህ፡፡ (ጆርጅ ኦርዌል፣ “1984”)

 

 

1 WAR IS PEACE

FREEDOM IS SLAVERY

IGNORANCE IS STRENGTH

comment pic

↧
↧

“ኢህአዴግ ከምሆን ሞቴን እመርጣለሁ” –ኢ/ር ዘለቀ ረዲ (ቃለምልልስ ከሎሚ መጽሔት ጋር)

$
0
0

Zeleke Redi
ኢ/ር ዘለቀ ረዲ ከወራት በፊት በተዋቀረውና አዲስ አመራሮችን በመረጠው አንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ውስጥ የውጭ ጉዳይ ኃላፊ ሆነው መመረጣቸው ይታወቃል፡፡ የሎሚ መፅሔት እውነትን ለህዝብ ለማድረስ ካለባት የሞያ ግዴታ አንፃር በኢ/ር ዘለቀ ዙሪያ በሚነሱ ሀሳቦች ላይ ተንተርሶ የሎሚ ም/አዘጋጅ ቶማስ አያሌው ያደረገውን ቆይታ የመጀመሪያ ክፍል እንደሚከተለው ቀርቧል፡፡

ሎሚ፡- አዲሱ የአንድነት ካቢኔ ሥራዎች እንዴት እየተከናወኑ ነው?

ኢ/ር ዘለቀ፡- በጣም ጥሩ ነው፡፡ ኢ/ር ግዛቸው በተለያዩ የአመራር ቦታዎች ላይ አዳዲስ ሰዎችን ነው ያመጣው፡፡ ከዛ አኳያ ጠንካራ ወይም ለቦታው ይመጥናሉ የተባሉ ሠዎች ናቸው የተመረጡት፡፡ ከዚህ ቀደምም ጠንካራ ሠዎች ነበሩ፡፡ አሁን ደግሞ የበለጠ ጠንካራ ሆነው ሊሠሩ የሚችሉ ሠዎች ናቸው የተመረጡት፡፡ እንደሚታወቀው አንድነት መሬት የረገጠ ፓርቲ ነው፡፡ ዝም ብሎ አየር ላይ የተንጠለጠለ ፓርቲ አይደለም፡፡ ከዛ አንፃር ሥራዎች በጥሩ ሁኔታ እየተከናወኑ ነው፡፡ አሁን ያለው አሠራር በዚሁ ከቀጠለ ጥሩ ውጤት ይመጣል የሚል እምነት አለኝ፡፡
ሎሚ፡- በርካቶች ግን አዲሱን የአንድነት ካቢኔ አወቃቀር አልወደዱትም ይባላል፤

ኢ/ር ዘለቀ፡- ከምን አንፃር?…ግልፅ አድርግልኝ?

ሎሚ፡- አንተን ጨምሮ ሌሎች ሁለት ሶስት ሰዎችን ማካተቱ ትክክል አይደለም የሚሉ ሂሶች ተሰንዝረዋል፡፡ ለምሳሌ፡- አንተን ከፓርቲው ለረጅም ጊዜ ርቆ ነበር፤ ራሱንም ማግለሉንም ተናግሮ ነበር፡፡ ቀደም ሲል በአመራርነት በነበረበት ጊዜ ድክመት ታይቶበት ነበር፡፡ እንደዚህ ዓይነት ችግሮች ያሉበት ሠው እንዴት በአመራር ደረጃ ሊመረጥ ይችላል የሚሉ ወገኖች አሉ፤

ኢ/ር ዘለቀ፡- አንዳንድ ነገሮችን ግልፅ ላድርግልህ፡፡ በመጀመሪያ ከፓርቲው ርቆ ነበር የሚለው ስህተት ነው፡፡ የፓርቲው አባል ነኝ፤ ከፓርቲውም ራሴን አላገለልኩም፤ ከስራ አስፈፃሚነት ራሴን አግልዬ ነበር፤ ከፓርቲው ግን አላገለልኩም፡፡ በብሔራዊ ም/ቤት ውስጥ እሰራ ነበር፡፡ በአባልነትም ቢሆን እሰራ ነበር፡፡ ሁልጊዜ ከፓርቲው ጋር እሰራ እንደነበር ነው የማስበው፡፡ ከፓርቲው ርቆ ፓርቲውን ለቆ ተመልሶ ወደ አንድነት መመለስ ትንሽ ከባድ ነው፡፡ አንድነት እንደ ሌሎች ፓርቲዎች አይደለም፡፡ አንድነት በጣም በነፃነት የሚሰራበት ፓርቲ ነው፡፡ እውነት ነው የምነግርህ፤ እኔ አንድነትን ለማስተዋወቅ አይደለም፡፡ ለምሳሌ ኢ/ር ግዛቸው ዛሬ ተነስቶ እኔ መስራት አይችልም ቢል ለምን የሚል ጥያቄ እንኳን አይቀርብበትም፡፡ እሺ ነው የሚባለው፡፡ ከአንድነት ሥራ አስፈፃሚው እለቃለሁ ሲል ለምን ትለቃለህ ብሎ የሚጠይቅ አልነበረም፡፡ መብትህ ነው፡፡ ማንም ሰው ከአባልነት እለቃለሁ ካለ የመልቀቅ ሙሉ መብት አለው፡፡ እመለሳለሁ ካለም ደግሞ ትቀበለዋለህ፡፡ ከፓርቲው ርቆ የነበረ ሰው ድጋሚ ልመለስ ቢል ትንሽ ከባድ ነው፡፡ አባላቱ ከባድ ናቸው፡፡ ብሔራዊ ም/ቤቱም እንደዚህ እንደምንገምተው አይደለም፡፡

ሎሚ፡- ከዚህ ቀደም ለሰንደቅ ጋዜጣ በሰጠኸው ቃለ ምልልስ ከስራ አስፈፃሚነት በራስህ ፍቃድ መልቀቅህን ተናግረህ ነበር፡፡ የፓርቲው ሊ/መንበር የነበሩት ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ ደግሞ አንተን ከቦታው ያነሱት እርሳቸው መሆናቸውን ይናገራሉ፡፡ ይሄን ነገር እንዴት ተመለከትከው?

ኢ/ር ዘለቀ፡- በዚህ ጉዳይ ምንም ባልል ደስ ይለኛል፡፡ ከዚህ ቀደም በእናንተ መፅሔት ላይ እርሳቸው ያሉትን አይቼዋለሁ፡፡ የመፅሔታችሁ ደንበኛ ነኝ፡፡ እርሳቸው እኔ ነኝ ያነሳሁት ብለዋል፡፡ ጥሩ፤ እርሳቸውም ያባሩኝ እኔም ልልቀቅ ችግር የለውም፡፡ አንድነት በነበሩበት ጊዜ ስለሰሩት በጎ ነገር አውርተዋል፡፡ ከበጎ ነገሮች አንዱ ደግሞ እኔን ማባረር ነው፡፡ ከዚህ ላይ ሊያገኙት የሚችሉት ትርፍ ምንድን ነው? እኔን የመሰለ ሠው፣ ራሱን ችሎ የሚንቀሳቀስ፣ የራሱ ሥራ ያለው፣ ፓርቲውን ሊደግፍ የሚችል ሰው ማባረራቸው ነው ውጤታማ ሥራቸው? በጣም በርካታ ሠዎችን አስገብተው እነገሌን አምጥቻቸዋለሁ ማለት ነው የሚሻለው ወይስ ኢ/ር ዘለቀን አባርሬዋለሁ?! እሺ እርሳቸው አባረሩኝ ብዬ ልውሰድ፤ ሰንደቅ ጋዜጣ በገዛ ፈቃዴ መልቀቄን ተከትሎ ጠይቋቸው ነበር፡፡ ያኔ “ኢ/ር ዘለቀ አለቀቀም፤ ሥራ እየሰራ እንደሆነ ነው የምናውቀው፡፡ አልሄደም አለቀቀም” ብለው ምላሽ ሰጥተዋል፡፡ በርሳቸው ዕድሜ ያለ ሰው ያንን ምስክርነት መካድ ይችላል?…ያኔ የተናገሩት ነገር መረጃ ነው፡፡ ወደኋላ ተመልሰው እኔን አባረውኝስ ቢሆን? መናገራቸው ምንድነው ትርፉ? እኔና እርሳቸው በዕድሜ በእጥፍ እንለያያለን፡፡ በዕድሜያቸው ብዙ ችሎታ አላቸው፤ ብዙ ለፍተዋል፡፡ ውጤት ማምጣት አለማምጣት የራሱ ጉዳይ ሆኖ ማለት ነው፡፡ እኚህ ሠው እኔ እንኳን በጣም መጥፎ ሠው ሆኜ ባስቸግር እንኳን መልሰው በጣም መጥፎ ሰው ነበር፤ እኔ ነኝ ያስተካከልኩት ቅርጽ ያስያዝኩት ቢሉ ነበር የሚሻለው፡፡ ኢ/ር ዘለቀን ያባረርኩት እኔ ነኝ ማለት ጀብደኝነትም አይደለም፡፡

አንድ ሰው ሊቀ-መንበር የሚሆነው ሰዎችን ለማባረር አይደለም፡፡ ደካማውን ማጠንከር ይጠበቅበታል፡፡ ማንም ሠው ደካማ ሊሆን ይችላል፡፡ እኔ በተፈጥሮዬ ደካማ አይደለሁም፡፡ ደካማ ብሆን ኖሮ አሁን ያለሁበት ቦታ ላይ አልገኝም ነበር፡፡ በትንሹ 150 ሠራተኞችን በስሬ አስተዳድራለሁ፡፡ ከ40 በላይ ቋሚ ሠራተኞች አሉኝ፡፡ ከ200 ሺህ ብር በላይ የወር ደመወዝ እከፍላለሁ፡፡ ይሔን ሁሉ የሚሰራ ሰው ደካማ ነው? ቤተሰቤንም ሆነ ሌሎች ሠዎችን ማስተዳደር የምችል ሠው ነኝ፡፡ ደካማ ብሆንም ከዶ/ር ነጋሶ የምጠብቀው “እንደዚህ ያለ ደካማ ነበር፤ እኔ ነኝ ጠንካራ ያደረግኩት” የሚል ምላሽ ነበር፡፡

ሎሚ፡- የአንድነት የዲሲፕሊን ኮሚቴ ሊቀጣህ የነበረበትና እንዲቀጣህ መመሪያ የተላለፈበት ሁኔታ ነበር?…

ኢ/ር ዘለቀ፡- ዶ/ር ነጋሶ ያላወቁት ነገር ሰው ወንጀለኛ ነው ጥፋተኛ ነው ተብሎ ሊከሰስ እንደሚችል ነው፡፡ አንድ ሌባ ፍርድ ቤት እስከሚፈርድበት ድረስ ተጠረርጣሪ እንጂ ወንጀለኛ አይባልም፡፡ ፍ/ቤቱ ትክክለኛ ውሳኔ እስከሚሰጠው ማለት ነው፡፡ የኔ ጉዳይም በዲሲፕሊን ያስቀጣል አያስቀጣም የሚለውን ማየት የነበረበት የዲሲፕሊን ኮሚቴ ነው አይደል? ያንን ዲሲፕሊን ኮሚቴ ደግሞ ማጠናከር የነበረባቸው ዶ/ር ናጋሶ ናቸው፡፡ እርሳቸው ያዳከሙትንና እርሳቸው የሌላቸውን ዲሲፕሊን ዲሲፕሊን ኮሚቴ ሊሰራው አይችልም፡፡ መጥተው ማቋቋም ይችላሉ፤ በሩ ክፍት ነው፡፡ እመጣለሁ ሲሉ አንድነት ይቀበላል፤ እሄዳለሁ ሲሉ ደህና ሁኑ ይላል፡፡ ጥፋት ኖሮብኝ ቢሆን ኖሮ እቀጣ ነበር፡፡ እርሳቸው ግን ውጭ ሆነው ይቆጫቸዋል፡፡ የኔ አለመቀጣት ትርፉን አላውቀውም፡፡ ፍ/ቤትም አለ እኮ፤ ከዛ ባለፈም እኔን መክሰስ ይቻላል፡፡ እኔ በእውነቱ የዲሲፕሊን ግድፈት አልነበረብኝም፡፡ ም/ቤቱ ዲሲፕሊን ኮሚቴ ይየው ብሏል አይደል? ይሄ ማለት ደግሞ ዘለቀ የዲሲፕሊን ግድፈት አለበት ማለት አይደለም፡፡ ዲሲፕሊን ኮሚቴውን አጠናክሮ እኔን ወደ ዲሲፕሊን ኮሚቴ ማቅረብ የነበረባቸው እርሳቸው ነበሩ፡፡ እውነት ለመናገር በእናንተ መፅሔት ላይ እንዳየሁት እኔ በፓርቲ መቀጠሌ ደስተኛ አላደረጋቸውም፡፡ እኔ ለቅቄ እወጣላቸዋለሁ፤ ችግር የለውም፡፡ ውጭ ሆኜ ፓርቲዬን መርዳት እችላለሁ፡፡ ዋናው ግን የሚያገኙት ትርፍ ምንድነው የሚለው ነው፡፡

ከመንግስት በኩል ብዙ ጫና አለብኝ፡፡ የኮንስትራክሽን ድርጅቴ ስምንት ዓመት ሆኖታል፡፡ እስካሁን ድረስ ግን ከመንግስት ሁለት ጊዜ ብቻ ነው የስራ ዕድል ያገኘሁት፡፡ ማንኛውም ኮንትራክተር የኮንደሚኒየም ሥራ የሚሰጠው ተጠርቶ ነው፡፡ የእኔ ድርጅት ግን ኮንዶሚኒየም ላይ አንድ ጠጠር አልጣለም፡፡ ለምን ቢባል ሊያዩኝ ስላልፈለጉ ነው፡፡ የኔ አንድነት ውስጥ መቀጠል ለምን ዶ/ር ነጋሶን ያበሳጫቸዋል? የሶስት ወር ጊዜ ነው የተሰጠን፡፡ አቅም ከሌለኝ የአንድነት ድርጅት አመንክም አላመንክም በሶተኛው ወር ዘለቀ አቅም የለውምና ይውጣ ይላል፡፡ ያንን ጊዜ መጠበቅ ያስፈልጋል፡፡ ዶ/ር ነጋሶ ከኢህአዴግ ጎራ የወጡ ሰዎችን የዲሞክራሲው ትግል አጋር ማድረግ ነበረባቸው፡፡ እንጂ እኔም ላግዝ ብሎ የመጣውን የኔ ዓይነት ሰው አባረርኩት ማለት አይጠበቅባቸውም ነበር፡፡

ሎሚ፡- የአንድነት ፓርቲ የውጪ ግንኙነት ኃላፊ ነህ፡፡ ቦታው ትልቅ ነው፤ ይህንን ትልቅ ቦታ ያገኘኸው ደግሞ ፓርቲያችሁ አንድነት የሚሊዮኖች ድምፅ ለነፃነት የሚለውን እንቅስቃሴ ባዘጋጀበት ወቅት የገንዘብ ልገሳ ስላደረገ ለውለታው የተሰጠው ነው እንጂ ለቦታው የሚመጥን ሆኖ አይደለም ሲባል ነበር፤

ኢ/ር ዘለቀ፡- በርግጠኝነት ይሄን የሚሉ አዕምሮ ያላቸው ሠዎች ይኖራሉ ብዬ አልገምትም፡፡ ይሄ አንድነትን መናቅ ነው፡፡ አንድነት የት ቦታም እንዳለም አለማወቅ ነው፡፡ እውነቴን ነው የምነግርህ አንድነት ለብር ብሎ በህልውናው ላይ የሚደራደር ፓርቲ አይደለም፡፡ ይሄ የአዕምሮ ማነስም ጭምር ነው፡፡ ይሄ ማለት ዘለቀ አንድነትን በብር ይገዛዋል ብሎ ማሰብ ነው፡፡ አንድነትንም ማናናቅና መወንጀልም ጭምር ነው፡፡ የአንድነት ም/ቤት በሃገር፣ በህዝብ፣ በህልውና ላይ የማይደራደር ም/ቤት ነው፡፡ ዶ/ር ነጋሶ ሊቀ-መንበር በነበሩበት ጊዜ በአብላጫ ድምፅ የሚወሰነውን ነገር የመስራት ግዴታ አለባቸው አይደል? የራሳቸውን ልዩነት ግን በጋዜጣ ሁሉ ያራግቡ ነበር፡፡ ስለመድረክ ጉዳይ ልዩነት አለኝ ብለው ይፅፋሉ፡፡ ልዩነታቸውን እየፃፉ በአብላጫ ድምፅ ለመገዛት ደግሞ ህጉ ያስገድዳቸው ነበር፡፡ ስለዚህ ዘለቀ ለሚሊዮኖች ድምፅ ገንዘብ ስላወጣ ነው የተመረጠው ብሎ አንድነትን መናገር አሳፋሪ ነው፡፡
ሎሚ፡- ኢ/ር ዘለቀ የኢህአዴግ መልዕክተኛ ነው የሚሉ ወገኖች አሉ፤ ለዚህ አባባላቸው ደግሞ ካሉት ሶስት ም/ጠ/ሚኒስትሮች መካከል አንዱ የሆኑት አቶ ሙክታር ከድር የቅርብ ወዳጅና ከወዳጅነትም በላይ በአንድነት ውስጥ የማዳከምና የአንድነትን እቅስቃሴ ለመቅጨት ሰርጎ እንዲገባ የተደረገ መልዕክተኛ ነው ይባላል፡፡ አንተስ ሰምተሃል? ምንስ ትላለህ?

ኢ/ር ዘለቀ፡- በመሠረቱ እነዚህን ነገሮች በሁለት ከፍዬ ማየት ነው የምፈልገው፡፡ እኔ የሙክታር ከድር ወዳጅ ብሆን እፈልገው ነበር፡፡ ለምን መሰለህ ሙክታርን እያነጋገርኩኝ መንግስት ያለውን አቋም ማወቅ እችል ነበር፡፡ እውነት ለመናገር እንደዚህ ያሉ ሠዎችን አጥተን ነው እንጂ ከመንግስት ከፍተኛ ባለስልጣናት ጋር ጓደኛ ብንሆን እኮ ብዙ ነገር ታወራለህ፡፡ ድክመቱንም የምታገኘውም በዛ ነው፡፡ ኢህአዴግ እኮ ደርግን ያሸነፈው በደህንነቱ በእነ ተስፋዬ ወ/ስላሴ አማካይነት ነው፡፡ ቁልፍ ሰዎችን መያዝ ያስፈልጋል፡፡ ብንይዛቸው ደግሞ ይህ የድክመት ምልክት አይደለም፡፡ ምናልባት እንግዲህ ሙክታርም የጅማ ልጅ ነው፤ እኔም የጅማ ልጅ ነኝ፤ ያው መላ ምት ነው፡፡

እንደ ዶ/ር ነጋሶ ያሉ በርካታ ሠዎች የሚጎነትሉህ ቦታ ቁጭ ብለህ የኢህአዴግ መልዕክተኛ ከምትሆን የኢህአዴግ ካድሬ አትሆንም? የአንድ ዞን አስተዳዳሪነት ቦታ ይሰጥሃል እኮ፡፡ አሁን ካሉት ሠዎች በአቅም ላልተናነስ እችላለሁ፡፡ ኦህዴድ ብሆን ደረጃዬን ጠብቄ መጥቼ ሙክታር ያለበት ደረጃ መድረስ እችል ነበር፡፡ በርግጠኝነት ዛሬ ሄጄ ብጠይቀው ኢህአዴግ ይሄን የሚነፍግ ንፉግ አይመስለኝም፡፡ እንደውም ጠላት መቀነስ ነው፡፡

ለህሊናቸው ሳይሆን ለሆዳቸው ያደሩ ጋዚጠኞችም አሉ፡፡ አንድ ሁለት ሶስት ጋዜጠኞች ደውለውልኝ አንድ ጥያቄ ጠይቀውኝ ነበር፡፡ በጣም የወረደ ጥያቄ ማለት ነው፡፡ እኔ ብዙ አልፈራም፤ ሠዎች ይመጡና አንድ ነገር እንስራ ይሉሃል፡፡ በሁለተኛው ቀን ሌላ ነገር ይጠይቁሃል፡፡ ይሄማ ትክክል አይደለም ስትላቸው እንደዚህ ነህ እንልሃለን ይሉሃል፡፡ ምንም ይበሉህ ምን ጊዜውን ጠብቆ እውነት ያወጣዋል፡፡ እኔ ከአንድነት ስራ አስፈፃሚ እንደወጣሁ ኢህአዴግ ሊሆን ነው ምናምን ይሉ ነበር፡፡ ኢህአዴግ እኔ የማስበውን የሚያስብ ከሆነ እንደኔ አንድነት የሚያጠናክር ከሆነ ልናግዘውና ልናጠናክረው ነው የሚገባው፡፡ እንደኔ ዓይነት ኢህአዴጎች ካሉ ለምንድነው የማንሠበስባቸውና የማናመጣቸው? ዘለቀ የኢህአዴግ አባል ሲሆን መታወቂያ ይኖረዋል አይደል፡፡ ኢህአዴግ አንድነትን ለመሠለል ከበቃ አድገናል ማለት ነው፡፡ ይቺ አሉ የሚባሉትን ሠዎች ከስር ሆኖ መቀንጠሻ ናት ዘዴ ናት፡፡

ስለ አንድ ሰው ልንገርህ፤ የባንክ ሠራተኛ ነው፤ ስሙን አልገልፅልህም፤ መሃንዲስ ነው፡፡ አንድ ቀን በራሴ ፅሁፍ በይፋ እገልጸዋለሁ፡፡ አንዱን ጋዜጠኛ ምን ብሎ ያሳስተዋል መሠለህ? አርሲ ነገሌ “መንገድ ስራ” ወስደነው ነበር፡፡ መንገዱ ፈርሶ ተበላሻሽቶ ከፍተኛ ብጥብጥ ተነስቷል ብሎ ይነግረዋል፡፡ ይሄን የሰማው ልጅ ይደውልልኝና “ኢ/ር ዘለቀ ነህ አዎ…አርሲ ነገሌ የምትሠሩት መንገድ ተበላሽቷል ወይ? ምናምን ብሎ ይጠይቀኛል፡፡ ማን ነገረህ? አልኩት፡፡ ጥቆማ ደርሶን ነው አለ፡፡ ዓይተህ ማውጣት ትችላለህ፤ ይህን ካላደረግክ እኛ ህጉን ጠብቀን እንከስሃለን ብዬ መለስኩለት፡፡ ከ15 ቀን በኋላ መንገዱ ይመረቅ ነበር፡፡ ከመመረቁ በፊት ተዟዙሮ የተመለከተው የከተማው አስተዳደር “የመጀመሪያ ኮንትራክተር ነው” ብሎናል፡፡ ሞያውን ተጠቅሞ ስራውን በአግባቡ ሰርቶልናል ተብሎ የከተማ አስተዳደሩ “ቡልኮ” ሸልሞኛል፡፡ በኦሮሞ ባህል ቡልኮ የተሸለሙት እነ አባዱላ ናቸው፡፡ ጋዜጠኛው እዛ ነበርና በጣም ነው የደነገጠው፡፡ ስለዚህ እዚህ መጥተው የተለየ ጥቅም የሚያገኙ ሠዎች ሄደው ስም ያጠፋሉ፡፡ ኢ/ር ግዛቸውን ብዙ ነገር ይሉታል፡፡ ኢ/ር ግዛቸው በተፈጥሮው ጠንካራና እያጣራ ማለፍ የሚወድ ሠው ነው፡፡ ዶ/ር ነጋሶ ቢሆኑ በዚህ ፈተና ይወድቁ ነበር፡፡

ዶ/ር ነጋሶ ጋር ቀድሞ ሄዶ የነገራቸው ሰው አሸናፊ ነው፡፡ እኔ አንተን ቀጥቅጬህ ቀድሜ ሄጄ ከነገርኳቸው ቁስልህን ብታሳይ አይሰሙህም፡፡ ኢ/ር ግዛቸው ግን ይህንን ሁሉ ነው የተቋቋመው፡፡ እነዚህ ሠዎች ካንተ ጥቅም ሲያጡ ፓርቲ ውስጥ ስትገባ የምትጠቀም ይመስላቸዋል፡፡ ለሃገርህ የሆነ አስተዋፅዖ ለማበርከት የሄድክ አይመስላቸውም፡፡ ከዚህ አንፃር ብዙ ነገር ሊወራብህ ይችላል፡፡ በመረጃ “ኢህአዴግ ነው ብሎ” የሚሞግተኝ ካለ ምንም ችግር የለብኝም፡፡ አሉባልታ ግን አሉባልታ ነው፡፡ የኔ ማረጋጋጫ ስራዬ፡፡ ኢህአዴግ ብሆን ኖሮ አንዲት ሴትዮ 400 ሺህ ብር በልታኝ አትቀርም ነበር፡፡ ኢህአዴግ ሆኜ ይሄ ነው የኮንዶሚኒየም ግንባታ ላይ እንዳልሳተፍ (እንዳልሰራ) አልደረግም ነበር፡፡ ኢህአዴግ የሆኑ ሰዎችን እናውቃቸዋለን፡፡ ቢጠሯቸው አይሰሙም፡፡ ገንዘባቸው የት ነው ያለው? እኛ እኮ NGO እየለመንን ነው የምንሰራው፡፡ ያውም ደግሞ ጠንካራ ጠንካራ NGOዎች ናቸው እንጂ አነስ አነስ ያሉት ዝም በሉ ሲባሉ ዝም ይላሉ፡፡ በርካታ NGOዎች ናቸው ጨረታ ካለፍን በኋላ የሰረዙብን፤ ደህንነቶች እያስፈራሯቸው ማለት ነው፡፡ ዘለቀ ኢህአዴግ ነው የሚባለው ከአንድነት ከፓርቲ አገልግሎት ለማስወጣት ሲባል ነው፡፡ ኢህአዴግ መሆን ብፈልግ በአንድነት በኩል መዞር የሚጠበቅብኝ አይመስለኝም፡፡ ለሰራተኞቼ ከ5 ሚሊዮን ብር በላይ ኢንሹራንስ የምገዛ ሰው ነኝ፡፡ አንድ ሚኒስትር የሚከፈለው ደመወዝ ስንት ነው? እኔ እኮ 38 ሺህ ብር ነው ለአንድ መሃንዲስ የምከፍለው፡፡ ምን አጥቼ ነው ኢህአዴግ ስር የምሸጎጠው? በህልሜም የኢህአዴግ አባል ሆኜ ማየት አልፈልግም፡፡ እስካሁን ባለኝ አቋም የኢህአዴግ አባል አይደለሁም፡፡ የአይዲዎሎጂ አስተሳሰብ ጊዜውን ጠብቆ የሚቀየር ነገር ነውና ወደፊት ምን እንደሚፈጠር አላውቅም፡፡ ምኒልክም “ሃገሬ ስትወረር ከማይ ሞቴን እመርጣለሁ” እንዳሉት እኔም ኢህአዴግ ከምሆን ሞቴን ነው የምመርጠው፡፡ የሚሊዮኖች ድምፅ ለነጻነት የሚለውን የአንድነት ዘመቻ ረዳህ ተባልኩ፡፡ ግድቡ ለኢትዮጵያ ጥቅም ሲሰራ እደግፋለሁ፡፡ ኢህአዴግ የፖለቲካ ቅስቀሳ ስለሚያደርግበት አንድም እርዳታ አድርጌበት አላውቅም፡፡ የአባይ ግድብ የኔ ገንዘብ የለበትም፡፡ ለምን? ለፖለቲካ ቅስቀሳ እያዋለው ስለሆነ፡፡ ለህዝብ አሳልፎ ስላልሠጠ፤ ለህዝብ ስጥ እያልኩ እየፃፍኩበት ነው፡፡ ለህዝብ ሲሰጥ ግን አንደኛ የምረዳው እኔ ነኝ፡፡ አሁን ግን ለአባይ ግድብ የአንድ ብር ቦንድ አልገዛሁም፡፡

ሎሚ፡- ከዚህ ቀደም የፓርቲያችሁ ልሳን የሆነው ፍኖተ ነፃነትን “አዲስ ዘመን” ብለህ ዘልፈኸዋል፤ አዲሱ ካቢኔ ሲዋቀርም በአንተ መመረጥ ዙሪያ ከተነሱ ቅሬታዎች አንዱ ይሄነው፤ እንዲህ ልትል የቻልክበት ምክንያት ምንድነው?

ኢ/ር ዘለቀ፡- ምን መሰለህ? በወቅቱ አንድ ዜና ሰርተው ነበር፡፡ እኔን የሚመለከት ዜና ም/ቤቱ ሲሰጣቸው ሚዛናዊ ለማድረግ ሀሳቤን አላካተቱም ነበር፡፡ ስላልጠየቁኝ “ፍኖተ ነፃነት” ትልቅ የህዝብ ሚዲያ ናት፤ ግን ምንድነው ከአዲስ ዘመን የተለየ የሚያደርገው?…አዲስ ዘመን ዜና ሲሰራ የጉዳዩን ባለቤት አይጠቅም አይደል?…ፍኖተ ነጻነትም እንደዚያ ስላደረገ አዲስ ዘመን ብዬው ነበር፡፡ እኔን መጠየቅ ነበረባቸው፡፡ በአንድነት ባህል አንድ ግለሰብ ከፕሬዚዳንቱ እኩል መብት አለው፡፡ ያንን መብቴን አልሰጣችሁኝም የሚል ቅሬታ ነው ያነሳሁት፡፡ ከጋዜጠኛው ጋርም ተነጋግረናል፡፡ ዜናውን ስትሰሩ ሚዛናዊ ማድረግ አለባችሁ በሚል ተወያይተናል፡፡ ችግሩም በሰላም ተፈትቷል፡፡

↧

አስማተኛው የኢኮኖሚ እድገት! (በ ገብርኤሉ ተስፋዬ)

$
0
0

ከየት ጀምሬ ወደየት እንደምሄድ አላውቀውም፣ አሁን አሁን የእድገት መለኪያው ምን እንደሆነ እንኩዋን ግራ ገብቷችዋል:: ወይስ የኢኮኖሚ እድገቱ ለኢትዮጲያውያን ሳይሆን ኢትዮጲያን ለሚያስተዳድሯት ብቻ ነው ወይ? እውነቱ በገሀድ ግልፅ ብሎ እያለ ካለፉት አስር አመታት ጀምሮ ጆሮዋችንን በሁለት ዲጅት ሀገሪቱ አድጋለች እያሉ ሲያደነቁሩን ከረሙ:: ለኔ እድገት የሚለው ቃል በአሁን ሰሀት ስድብ መስሎ እየታየኝ ነው:: የተወሰኑ ሰዎች ብር በብር ላይ አካበቱ፣ሀፍታም ሆኑ፣ ህንፃ ገነቡ፣ከመኪና መኪና ቀያየሩ ወዘተ እየተባለ  በኢትዮጲያ ስም መነገዱ አግባብ አይደለም:: ለመሆኑ የኢትዮጲያ ህዝብ ጠግቦ የሚበላው ሀሁን ነው ወይስ የዛሬ 10 እና 20 አመት በፊት ነው? መልሱን የሁላችንም ልቦና ያውቀዋል! ህዝቡ አንገቱን ደፍቶ ሁሉን ነገር ሰምቶ እንዳልሰማ  አይቶ እንዳላየ ዝም ሲል ጅል የሆነ መሰላችው:: እስቲ የኢትዮጲያ እድገት ተብየው ያመጣውን ለውጥ ለመመልከት ልሞክር::

በመጀመሪያ መመለከት የምፈልገው የምግብ ዋስትናን ነው::የምግብ ዋስትና ማሽቆልቆሉን የማያምኑ ለሆዳችው የሞቱ እነሱ ብቻ ሲበሉ ሌላውም የበላ የሚመስላችው ብዙ አሉ:: ሆኖም ግን እውነት እውነት ነች እና ምንም ምንም ቢሉ እውነትነቷን  አትቀይርም:: ስለምግብ ዋስትና ለመናገር በአዲስ አበባ ስለሚኖረው ህዝብ መናገርን መረጥኩ ምክንያቴም አዲይስ አበባ የኢትዮጲያ ዋና ከተማ እንደ መሆኑዋ መጠን፣የኢህአዴግ አመራሮች ስለእድገት ሲያወሩ የሚጠቅሱዋት ከተማ ስለሆነች እና በጣም ብዙ ህዝብ(ከ 5 እስከ 6 ሚልየን) ስለሚኖርባት ነው:: እዝይጋ ሥራ አልባ የሆኑትን፣ሚበላ የሌላችውን ብዙዎቹን የማሀበረሰባች አካላትን ሳይሆን ማየት የምፈልገው ስራ አገኘው ብሎ በመንግስት መስሪያቤት ተቀጥሮ የሚሰራውን ነው:: አንድ የመንግስት ሰራተኛ የድግሪ ምሩቅ የሆነ በወር 1600 ብር የሚያገኝ ሲሆን ከዚያ ላይ 250 እስከ 300  ግብር ይከፍላል በእጁ ላይ 1300 ይቀረዋል እንበል ፣ የቤት ኪራይን በተመለከት በአሁን ሰሀት በአዲስ አበባ አንድ ክፍል ቤት በትንሹ ከ 700 እስከ 800 ብር የሚያወጣ ሲሆን ከ 1300 ላይ ይሄን ብር ስናነሳ  500 ብር አካባቢ ይቀረዋል፣ በየቀኑ ለትራንስፖርት በትንሹ 3 ብር አወጣ ቢባለ 400 ብር እጁ ላይ ቀረው ማለት ነው:: እስቲ ይሄ ሰውዬ ሙሉ ጤነኛ ነው የህክምና ወጪ አያስፈልገው ቤተሰብ (ልጆችም) የሉትም ብንል እንኳን 400 ብር አያምስት ኪሎ ጤፍ ወይም 4 ኪሎ ሥጋ በወር አይገዛለትም:: በአስማት መኖር ማለት ይሄ ነው!! በየቦታው እንደምንሰማው  ከ100,000 በላይ የጎዳና ተዳዳሪዎች በአዲስ አበባ ብቻ ይገኛሉ:: እነሱም ከእድገቱ ጋር  ነው አብረው የመጡት እያሉን ነው! ብሎ ብሎ ጉርሻ መሸጥ የተጀመረበት አገር እድገት አለ ከሚሉ አስማት አለ ቢሉ ይሻላል::እርግጥ ነው የተወሰኑ ሰዎች በአዲስ አበባ  የምግብ ዋስትናችው የተጠበቀ ነው  ከነርሱም ብዙወቹ የገዝው ፓርቲ አባላት ናችው:: እና ስለ እድገት ሲወራ የኢትዮጲያ ህዝብ በልቶ ጠግቦ አደረ  የሚለው ተረት ባይተረክ መልካም ነው እላለው::

በመቀጠል ማየት የምፈልገው ማንኛው የምራባውያን ሀገር የኢኮኖሚ እድገት መጣ ብለው ሲያወሩ ለማሀበረሰባችው የተሻለ የስራ እድልን ፈጥረው ሲገኙ ነው:: በአሁን ሰሀት አብዛኛው የኢትዮጲያ ወጣት የት ነው የሚገኘው ጫት ቤት፣ መጠጥ ቤት፣ሺሻ ቤት፣ ወይስ ኑሮውን ለማሸነፍ ከሀገር ወቶ ተሰዶ በረሀ በልቶት ቀርቷል:: ማንም በአገሩ መኖርን የሚጠላ የለም! ወጣቱ ከሀገር ተሰዶ ሲወጣ ነጮቹ ናፍቀውት አይመስለኝም:: ከሀገር ተሰዶ በረሀ ላይ መሞት እንዳለ፣ በሀር ውስጥ የሻርክ እራት መሆን፣መደፈር፣ ከህንፃ ላይ ተወርውሮ መሞት አልፎ ተርፎም የሰውነት አካላችው እስከመሸጥ እንደሚደርስ እያወቁ ሀገራችውን ጥለው የሚሄዱት ቁጥር መጨመሩ ምንን ያሳያል? ምን ያህል ወጣቱ በኢህአዴግ አመራር እንደተማረረና  ተስፋ እንደቆረጠ ነው የሚያሳየን:: ሌላው የሴት እህቶቻችን ቁጥር በወሲብ ንግድ ላይ እየጨመረ መሄዱ በካንፓስ ደረጃ መርጠው  የተማሩት ፊልድ ነው ብዬ አላምንም ለኔ ይሄ የሚያሳየው ወጣቱ ከስራ ማጣት የተነሳ ኑሮን ለማሸነፍ የማይፈልገው አዝቀጥውስጥ እየገባ እንዳለ ነው:: ከሰሞኑ ደግሞ  ይባስ ብሎ እድሜያችው ከ18 አመት በታች የሆኑ ልጅ አገረዶችን በየድረ ገጹ ለወሲብ ሽያጫ አቅርበዋል፣ የሚገርም ነው እዚም ዘመን ላይ ደረስናል ያስብላል!

Yeweyane firewoch

በሶስተኛ ደረጃ ማየት የምፈልገው ከምግብ ውጪ ለሰው ልጅ መሰረታዊ ነገሮች ብዬ የምላችውን የውሀና የመብራት አቅርቦትን ነው:: በአዲስ አበባ ከተማ የመብራትና የውሀ ነገር አነጋገሪ ከሆነ ሰንብቷል:: አብዛኛው የከተማው ክፍሎች ውሀና  መብራት በፈረቃ ነው የሚያገኙት:: ጥቁር አንበሳን የሚያህል ሆስፒታል በየህለቱ በጣም ብዙ በሽተኞችን የሚያስተናግድ ሆኖ ሳለ ለዚህ አይነቱ ችግር መጋለጡ በጣም አሳዛኝ ነው:: የእድገት አንዱ መሰረቱ የህዝብን የ መጠጥ ውሀ እና የመብራት አቅርቦት ማሟላት ወይም ስርጭቱን መጨመር ሲሆን በአዲስ አበባ የምናየው ነገር ግን የተገላቢጦሽ ነው::

የህዝቡን የምግብ ዋስትና ካልጠበቁ ወይም ካላሻሉ፣ ለወጣቱ የስራ እድል ማመቻችት ካልቻሉ፣ በቂ ወይም ተመጣጣኝ የውሀ እና የመብራት አቅርቦት መስጠት ካልቻሉ ታዲያ  የኢህአዴግ ባለስልጣናት ከህዝቡ ህየዘረፉ በሚወስዱት  ብር የሚገነቡት እንፃን በማየት ነው እድገት መጣ የሚባለው:: ኢትዮጲያ በየአመቱ በቢልየን ዶላሮች የሚቆጠር ገንዘብ በእርዳታ መልክ ታገኛለች ከዚህ ውስጥ ብዙው ገንዘብ የሚጠፋው በ ጥቁር ፕሮጀክት(Black project) ነው:: የ ጥቁር ፕሮጀክት ማለት መንግስት በህዝብ ስላልተመረጠ ስልጣኑን ለማቆየት ሲል  ለማሀበረሰቡ ብልፅግና የሚውለውን ገንዘብ ቀይሶ ለካድሬወችና  ለሰላዮች(ለሆድ አደሮች) እድሜውን ለማራዘም እንዲሁ የሚበትነው ብር ነው:: ከሰሞኑም እንደሰማነው መንግስት የተቃዋሚ ፓርቲን እና አባላታችውን ለመሰለል በሚልዮን ዶላር የሚቆጠር  የህዝቡን  ንብረት እንደሚጠቀም(እንደሚበትን) ተገልጿል::ሌላው በሀገሪቷ ውስጥ መጣ እየተባለ የሚያወሩለት የኢኮኖሚ እድገት መሰረት አልባ ስለሆነ መሰረታዊ ለውጦችን ሊያመጣ አልቻለም ይህን ልል   የቻልኩበት ምክንያት

1.  ስለኢኮኖሚ እድገት ሲወራ ብዙም ጊዜ ትኩረት  የማይሰጠው ግን ለኢህአዴግ ዋንኛው የገንዘብ ምንጭ የሆነው የስራአጥ እህትና ወንድሞቻችን በየሀገሩ የሚሰደድ ቁጥሩ በከፍተኛ ሁኔታ እየጨመሩ መሄዱ ነው::ይሄን ስል በአሁን ሰአት በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ኢትዮጲያን በየአገሩ ተበትነው የሚገኙ ሲሆን በየ ወሩ በሚሊዮን የሚቆጠር ዶላር ለቤተሰቦቻችው ይልካሉ:: በተዘዎዎሪ ይሄን ብር ኢህአዴግ የኢኮኖሚ እድገት ነው ይላለ:: ዕህት እና ወንድሞቻችንን በተለያዩ ሀገሮች በትኖ በነሱ ጀርባ ላይ ቁጭ ብሎ መሰረታዊ እድገት ሊመጣ አይችልም::

2. በመቶ ሺዎች  የሚቆጠሩ ህዝቦችን ለብዙ ሺ አመታት ከኖሩበት ቦታ አፈናቅሎ ለተለያዩ የእንድ እና የውጭ ሀገር ባለሀፍቶች መሬታችውን በመሸጥ የኢኮኖሚ እድገት አመጣን ማለት አይቻልም::እነዚ ሰዎች መሬታችው ሲወሰድ በመንግስት ብዙ ነገር ቃል የተገባላችው ቢሆንም አንዳችውም ግን እውን አልሆኑም:: በአሁን ሰሀት ከተወሰኑት በስተቀር በሙሉ በኬንያና በተለያዩ ቦታወች ተሰደው ሲገኙ በተቃራኒው ደግሞ የኢህአዴግ ካድሬዎች የከበሩበትን መንገድ እናያለን:: ማንኛውም አይነት እድገት በመጀመሪያ ደረጃ አላማ ሊያደርግ የሚገባው የመሀበረሰቡን ጥቅም ማስከበር ነው::

3. ምህራባዊያን(mainly US,UK and ISREAL) ኢትዮጲያ ያላት የጆክራፊ አቀማመጥ ቴሬሪስትን ለመዋጋት ያመቻል ብለው ስለሚያምኑና የኢትዮጲያ መንግስትም ጥቅሙን ለማስከበር አሽከር እንደሆነ ስላዩ  በየአመቱ የሚሰጡት እርዳታ እየጨመረ መሄዱ ይህን እና የመሳሰሉትን አጋጣሚወች በመጠቀም በኢትዮጲያ  እድገት አመጣው እያሉ ያወራሉ:: መሰረታዊ ችግሮች እየተባባሱ ህዝቡም ኑሮ እያሰቃየው፣ ወጣቱም ሥራ አልባ ሆኖ በየአረብ አገሩ እየተንከራተተ እድገት መጣ ማለት አይቻልም!! በሀገሪቷ ውስጥ የሚገባውን ገንዘብ በሙሉ ኢህአዴግ እና ካድሬዎቻችው አፍኖ በመብላት መሰረታዊ ለውጦች ሊመጡ አይችልም::  ስለዚህ ሁሉም ኢትዮጲያዊ የተሻለ አመራር  ያለው መንግስት ለማምጣት የበኩላችንን አስተዋጾ ማድረግ አለብን!!!!!!!!!

ፍቅር ለኢትዮጲያ ህዝብ!!!

አስተያየት ያላቹ በዚ ኢሜል ልታገኙኝ ትችላላቹ ( allforethiopia@gmail.com).

↧

መንበረ ጵጵስናውን እንግሊዝ ሀገር ለንደን ከተማ ያደረገው የሰሜን ምዕራብ አውሮፓ ሀገረ ስብከት ጽ/ቤት በሎንደን ከተማ ነዋሪ የሆኑትን «ቄስ» ብርሃኑ ብሥራትን ከሥልጣነ ክህነት አገልሎት መሻራቸውን አስታወቀ፤

$
0
0

 

«ቄስ» ብርሃኑ ብሥራትን

«ቄስ» ብርሃኑ ብሥራት

የዛሬ አርባ ዓመት ገደማ በአውሮፓ ለመጀመሪያ ጌዜ በቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔ፣ በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ቴዎፍሎስ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳ ዘኢትዮጵያ መልካም ፈቃድ በአባ አረጋዊ ወልደ ገብርኤል(ቆሞስ) በኋላ ብፁዕ አቡነ ዮሐን አስተዳዳሪነት ለረጅም ጊዜ መንፈሳዊ አገልግሎት ስትሰጥ በቆየችውና ቀጥሎም በእንግሊዝ ሀገር እና በመላው ዓለም በሚገኙ የጽዮን ወዳጆጅ ኦርቶዶክሳውያን ክርስቲያኖች የዘወትር ጸሎት፣  የጉልበትና የገንዘብ አስተጽዖ በአንድ ሚሊዮን ሰባት መቶ ሺህ የእንግሊዝ ገንዘብ በለንደን ከተማ ማዕከላዊ በሆነ ቦታ የራስዋ የሆነ ሕንጻ ቤተ ክርስቲያን ገዝታ ለሕዝበ ክርስቲያኑ የተሟላ አገልግሎት በመስጠት ላይ ትገናለች። ይሁን እንጂ የሕንጻው ክፍያ ከተጠናቀቀ በኋላ ጥቂት ግለሰቦች ቤተ ክርስቲያኑን ከቅዱስ ሲኖዶስ ማዕከላዊ አስተዳደር፣ ከቃለ ዓዋዲው መመሪያና ትዕዛዝ አስወጥተው በግለሰብ አደረጃጀት ሕንጻውን በግል ይዞታ ለመቆጣጠር ባወጡት የተሳሳተ ዕቅድና ዓላማ ምክንያት ችግር ተፈጥሮ መንፈሳዊ አገልግሎቱ በግፍ ተቋርጦ ቤተ ክርስቲያኑ ከዘጠኝ ወራት በላይ አላግባብ ተዘግቶ ካህናትና ምዕመናንን በከፍተኛ ደረጃ ሲያዛዝናቸውና ሲያስለቅሳቸው ቆይቷል።

 

በቤተ ክርስቲያኑ ውስጥ የተፈጠረው መንፈሳዊና ክርስቲያናዊ መንገድ ያልተከተለ፣ ከመጠን ያለፈና መረን የለቀቀ ረብሻ እጅግ በጣም በሚያሳዝን ሁኔታ በአብዛኛው በማኅበራዊ መገናኛ ብዙኃን ተዘግቦ በዓለም ላይ ያሉትን የቤተ ክርስቲይናችን ተከታዮች ሁሉ ያሳዘነ፣ በስደት የሚገኘውን የማኅበረሰባችን ገጽታ ያበላሸ አሳዛኝ ታሪክ ሆኖ የተዘገበ ተግባር ሲሆን፤ ቄስ ብርሃኑ ብሥራት የዚህ  ሕገ ቤተ ክርስቲያን የጣሰ፣ በቃለ ዓዋዲ የማይመራ የአመጽ ቡድን አስተባባሪና መሪ በመሆን  ለችግሩ ሁሉ ከፍተኛ አስተዋጽዖ ያደረጉና እያደረጉ የሚገኙ አርዓያነት የጎደላቸው ግለሰብ መሆናቸውን ካህናትና ምእመናን ሲያሳውቁ ቆይተዋል።

 

ቀደም ሲል የተፈጠረውን ችግር ለመፍታት በቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔ በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማቲያስ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ  ትዕዛዝ ብፁዕ አቡነ ገብርኤል እና ብፁዕ አቡነ ቀውስጦስ ወደ እንግሊዝ ሀገር ተልከው ከሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ እንጦንስ ጋር በመሆን ለችግሩ መፈትሄ ለመስጠት ከአንድ ወር በላይ ከፍተኛ ሙከራ ያደረጉ ቢሆንም ሊሳካ አልቻለም። ከአንድ ወር በላይ ለፈጀው የሰላም ጥረት አለመሳካት ምክንያቱ በ«ቄስ» ብርሃኑ ብሥራት እንመራለን የሚሉ ግለሰቦች ደንብ በማርቀቅ ስም «ፕሮቴስታንታዊ» ዓላማና አወቃቀር ያለው «መተዳደሪያ ደንብ» አርቅቀው ቤተ ክርስቲያኑን ለረጅም ጊዜ ተመዝግቦበት ከቆየው የቤተ ክርስቲያኗን ሃይማኖታዊ ልዕልና የማይጋፋ፣ ሕጋዊ የንብረትና ፋይናንስ ቁጥጥር ያለው የእንግሊዝ ሀገር የምግባረ ሰናይ (Charitable Trust) ምዝገባ  አስወጥተው፤ ኃላፊነቱ በተወሰነ የግል ኩባንያ (Private Company Limited by Guarantee) አስመዝግበው ሕንጻ ቤተ ክርስቲያኑን ለመቆጣጠርና የሚፈልጉትን ሁሉ ለማድረግ በቡደን ተደራጅተው ያወጡትን ዕቅድ መመሪያ አድርገው የሚንቀሳቀሱ በመሆናቸው እንደሆነ ተገልጿል። በዚህ ምክንያት ብጹዓን ሊቃለ ጳጳሳቱ በትዕግሥት የተቻላቸውን ያህል ቢሞክሩም ግለሰቦቹን ከስህተታቸው አስተምሮና አርሞ ወደ ሕገ ቤተ ክርስቲያን ለመመለስና የተፈጠረውን ችግር በመንፈሳዊ አስተዳደራዊ ዳኝነት ለመፍታት ካለመቻላቸውም በላይ፤ «ቄስ» ብርሃኑ ብሥራት የዚህ ሁሉ የተሳሳተና ከሕገ ቤተ ክርስቲያን የወጣ መንገድ ጠራጊ በመሆን፤ ሊቃነ ጳጳሳቱ የሰጡትን መንፈሳዊ መመሪያ ተግባራዊ ለማድረግ ፈቃደኛ አለመሆናቸው  ችግሩን ይበልጥ እንዳባባሰው ተገልጧል።

 

ብጹዓን ሊቃነ ጳጳሳቱ የተዘጋውን ቤተ ክርስቲያን ከፍተው በሐዘንና በልቅሶ ላይ ላሉት ምዕመናን መንፈሳዊ አገልግሎት ለመስጠት ሙከራ ቢያደርጉም፤ እነዚሁ ወገኖች የሌሎች እምነት ተከታዮችንና የፓለቲካ ቅራኔ አለን ብለው የተደራጁትን ሁሉ በማስተባበር በቤተ ክርስቲያኑ ግቢ ውስጥ ቅጥ ያጣ የረብሻና የሁከት ሰልፍ በማድረግ ቤተ ክርስቲያኑን እንዳይከፈት እጅግ በጣም አስቸጋሪና አሳዛኝ የሆነ ተግባር ሲፈጽሙ መቆየታቸው ተገልጿል።

 

ለሁለተኛ ጊዜ ሊቀ ጳጳሱ አቡነ እንጦንስ ነሐሴ 25 ቀን 2005 ዓ.ም (25/8/2013) ግራ ቀኙን ጎራ ለይተው በተሰበሰቡበት በቤተ ክርስቲያኑ ግቢ ውስጥ ተገኝተው «የተፈጠረውን ችግር በጠጴዛ ዙሪያ በሕገ ቤተ ክርስቲያን ይፈታ፣ ቤተ ክርስቲያኑ ያለምንም ቅደመ ሁኔታ ተከፍቶ መንፈሳዊ አገልግሎት ይከናወንበት» በማለት መንፈሳዊ መመሪያ ቢሰጡም ግለሰቦች ቤተ ክርስቲያንኑ እንዳይከፈት አመጻቸውን አጠናክረው  ሲያካሂዱ እንደነበረ በወቅቱ በመገናኛ ብዙኃን የተዘገበውን ማስረጃ በማድረግ ማብራሪያ ተሰጥቷል።

 

በመቀጠልም ብፁዕ አቡነ ገብርኤልና ብፁዕ አቡነ ያዕቆብ ከሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ ጋር በመሆን ለሦስተኛ ጊዜ ቤተ ክርስቲያኑን ከፍቶ አገልግሎት ለመስጠት ከፍተኛ ሙከራ ቢያደርጉም አሁንም የቤተ ክርስቲያኑን ሕንጻ በግል ባለቤትነትና ይዞታ ለመቀማት የተነሱት የቄስ ብርሃኑ ተከታዮች በፈጠሩት ኢ-ክርስቲያናዊ አመጽ ምክንያት ቤተ ክርስቲያኑን መክፈት ሳይቻል እንደቀረ ታውቋል።

በወቅቱ ቤተ ክርስቲያኑ እንዳይከፈት ለማደረግ የተደረገውን አመጽ፣ በሊቃነ ጳጳሳቱ ላይ የውረደውን የስድብ ውርጅብኝ፣ ባጠቃላይ ሁከቱንና እረብሻውን በቦታው ላይ ተገኝተው የተመለከቱት የደቡብ አፍሪካ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ያዕቆብ «በቤተ ክርስቲያን ሕይወቴ ክርስቲያን ቤተ ክርስቲያን ለጸሎትና ለቅዳሴ እንዳይከፈት ሲያውክ፣ ሰይጣን ሥጋ ለብሶ ሲንቀሳቀስ ያየሁበት ወቅት ቢኖር ይህ ነው» በማለት በጥልቅ ሀዘን ገልጸውታል።

 

የሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ ባለባቸው መንፈሳዊ ኃላፊነት ቄስ ብርሃኑ ብሥራትን በአካል አነጋግሮ መመሪያና ምክር ለመስጠት በተደጋጋሚ ሙከራ ቢያደርጉም፤ ቄሱ ግለስቦቹ በቤተ ክርስቲያን ላይ የሚያሳዩትን ፍጹም ሕገ ወጥ አመጽ እንደ ትልቅ ደጀን በመቁጠር ለመንፈሳዊ ጥሪው በጎ ምላሽ እንዳልሰጡ ታውቋል። ካህናትንም በሽምግልና መኖሪያ ቤታቸው ድረስ በመላክ የሚሄዱበት መንገድ ሁሉ ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያንን የጣሰ መሆኑን በመግለጽ የእናት ቤተ ክርስቲያንን ማከላዊ አስተዳደር ጠብቆ ወደማስጠበቁ በጎ ጎዳና እንዲመለሱ ቢጠየቁም ሊመለሱ እንዳልቻሉ ተብራርቷል።

 

ከዚያም አስቀደሞ ሰኔ 7 ቀን 2005ዓ.ም፣ ሐምሌ 24 ቀን 2005 ዓ.ም አንዲሁም ነሐሴ 15 ቀን 2005 ዓ.ም በተጻፈ ደብዳቤ ሊቀ ጳጳሱ ምክርና መመሪያ ለመስጠት ቢጠሯቸው ጥሪውን አክብረው ለመገኘት ፈቃደኛ አለመሆናቸው ተገልጧል። በጠቅላላው «ቄስ» ብርሃኑ ብሥራት ክህነቱን በመንፈሳዊ አደራነት ለሰጠቻቸው ቅድስት ቤተ ከርስቲያን ሕግጋትና ቀኖና ከመታዘዝ ይልቅ ግለሶቦቹን ስቶ በማሳት ከዛም አልፎ እነሱን በአዳራሽ በመሰብሰብ እራሳቸውን በራሳቸው በሕገ ወጥ መንገድ የቤተ ክርስቲያን አስተዳዳሪ አድርገው በመሾም፤ በሕዝብ የተመረጠውን ሰበካ ጉባዔ የቤተ ክርስቲያን ቁልፍ፣ ሀብትና ንብረት አስረክቡኝ የሚልና የሚያስገድድ ደብዳቤ መጻፋቸው የገለሰቡን ሕግ የመተላለፍ ተግባርና ከቤተ ክርስቲያን ሥርዓት ቁጥጥር ውጭ የሆኑ መሆኑን እንደሚያስረዳ በስፋት ተብራርቷል።

 

በሰሜን ምዕራብ አውሮፓ ሀገረ ስብከት መመሪያ፣ በደብሩ ሰበካ አስተዳደር ጉባኤ ያላሰለሰ ጥረት፣ “አቅሌስያ” በሚል ስም በተደራጁ ካህናት፣ ምዕመናንና የሰንበት ት/ቤት አባላት ድጋፍ፣ ከሕግ አማካሪ በተገኘ ብስለት የተሞላበት የሕግ ምክር፣ በአካባቢው ፖሊስና ጸጥታ ኃይሎች ቀና ትብብር ታህሳስ 20 ቀን 2006 ዓ.ም የእመቤተችን ቅድስት ድንግል ማርያም መታሰቢያ ውርኀዊ በዓል ዋዜማ ዕለት ቁጥራቸው ብዙ የሆነ ሕዝበ ክርስቲያን በተገኙበት ከዘጠኝ ወራት በላይ ከቄስ ብርሃኑ ብሥራት ጋር የጠበቀ ግንኙነት ያላቸው እነዚሁ ወገኖች ባስነሱት ኢ-ክርስቲያናዊ አመጽ ምክንያት በግፍ የተዘጋው ቤተ ክርስቲያን በብጹዕ ሊቀ ጳጳስ አቡነ እንጦንስ ቡራኬ ተከፍቶ በአራቱም ማዕዘን ወንጌል እየተነበበ ቅዳሴ ቤቱ ቀኖና ቤተ ክርስቲያን በሚያዘው መሠረት ተከፍቶ መንፈሳዊ አገልግሎቱን በይፋ እየተከናወነበት  መሆኑን የሀገረ ስብከቱ ጽ/ቤት አስታውቋል።

 

ቀጥሎም  በዘመነ አስተርዕዮ የሚከበሩት ዓበይት በዓላት የጌታችንና መደንኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የልደት፣ የጥምቀትና የእመቤታችን በዓላት ሁሉ በሊቀ ጳጳሱ መሪነት በብዙ ሺህ የሚቆጠር ምዕመናን በተገኙበት በለንደን ደብረ ጽዮን ቅደስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ታይቶ በማይታወቅ ታላቅ ድምቀትና አንድነት ተከብሯል። በተለይም የጥምቀቱ በዓል በለንደን ከተማ የሚገኙ አድባራት ታቦታት፣ ካህናት፣ ምእመናን እና የሰንበት ት/ቤት መዘምራን በአንድነት ሆነው “ጃንሜዳ በለንደን” የተባለለት ታላቅ የአንድነት በዓል የተከበረ መሆኑ ተዘግቧል። ይህ ሁሉ ሲሆን «ቄስ» ብርሃኑ ብሥራት  የቤተ ክርስቲያኑን ሕንጻ በኃይል ቀምተው በግለሰብ ይዞታ በገለልተኝነትና በግል ባለቤትነት ለመቆጣጠር የሚጓዙትን በማሳመጽ በግቢው ውስጥ ድንኳን በመጣል «በእኛ እምነት ቤተ ክርስቲያኑ አልተከፈተም» በማለት ሊቀ ጳጳሱ ከመሚመሩት ጉባዔ ከፍለው ከመሠረታዊው ኦርቶዶክሳዊ የሥርዓተ ሃይመኖት አፈጻጻም ተለይተው መዋላቸው ተረጋግጧል።

 

ቄስ ብርሃኑ ብሥራት በርዕሰ አድባራት ሎንደን ደብረ ጽዮን ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን ሊቀ ጳጳሱ ሥርዓተ ቅዳሴ እየመሩ ባለበት፣ መንፈሳዊ ትምህርት፣ ቃለ ምዕዳንና ጽሎተ ቡራኬ በሚሰጡበት ተመሳሳይ ሰዓት፤ ግለስቦችን ወደ ቤተ ክርስቲያን እንዳይገቡ በመከልከል በተመሳሳይ ጊዜ ሁለተኛ ተአምረ ማርያም፣ ሁለተኛ ኪዳን፣ ሁለተኛ ወንጌል፣ ሁለተኛ ሥርዓተ ቅዳሴ እያደረጉ፣ ቤተ መቅደስ ገብቶ ያልተባረከ ማዕጠንት እያጠኑ በቤተ ክርስቲያን የአንድነት መንፈሳዊ አገልግሎት በአንዲት ቤተ ክርስቲያን ውስጥ እጅግ በጣም ታይቶ የማይታወቅ መንፈሳዊነት የጎደለው፣ ክህነታዊ አርዓያነትና ኃላፊነት የተለየው ተግባር ሲፈጽሙ መቆየታቸው በስፋት ተብራርቷል።

 

ቄስ ብርሃኑ ብሥራት ከ1986 ዓ/ም ጀምሮ በብጹዕ አቡነ ዮሐንስ አሳሳቢነት፤ በብጹዕ ወዱስ አቡነ ጳውሎስ መልካም ፈቃድ ከመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት በጀት ተፈቅዶ በወቅቱ በአዲስ አበባ ከተማ ይኖሩ ለነበሩት ባለቤታቸውና ቤተ ሰቦቻቸው ጊዜው ይፈቅድ በነበረው መሠረት በወር ብር 500(አምስት መቶ ብር) ይከፈላቸው እንደነበር፣ እስከ ቅርብ ጊዜ ደረስ በርዕሰ አድባራት ለንደን ደብረ ጽዮን አራት እሁድ ብቻ ቀድሰው በየወሩ ከአንድ ሺህ አንድ መቶ ሰማንያ ሁለት የእንግሊዝ ገንዘብ  ቋሚና መደበኛ ክፍያ ይከፈላቸው እንደነበር ታውቋል። ነገር ግን ቄሱ ቤተ ክርስቲያኗ ከቅዱስ ሲኖዶስ ማዕከላዊ አስተዳደርና ከሀገረ ስብከት አመራር ተለይታ ገለልተኛ ሆና እሳቸው ብቻ ተጠቃሚ ለመሆን ባላቸው የተሳሳተ ዓላማ ምክንያት፤ ከአሁን በፊት ከመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ለሐዋርያዊ ተልዕኮ ወደ እንግሊዝ ሀገር ተልከው በሚመጡ አበው ሊቃነ ጳጳሳት፣ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን ላይ አድማና አመጽ በማስነሳት መንፈሳዊ ተልዕኳቸውን በአግባቡ እንዳይወጡ እንቅፋት ሲፈጥሩና ስቶ የማሳት ተገባር ሲፈጽሙ እንደቆዮ ስለመሆናቸው በሕይወተ ሥጋ ካሉት መካከል ብፁዕ አቡነ አትናቴዎስ፣ ብፁዕ አቡነ አረጋዊ፣ ብጹዕ አቡነ ገብርኤል፣ ብፁዕ አቡነ ቀውስጦስ፣ ብጹዕ አቡነ ኢሳይያስ፣ ሊቀ ካህናት ብርሃኑ ገብረ አማኑኤል፣ ንቡረ ዕድ አባ ወልደ ማርቆስ፣ እና ሌሎችም  በአስረጂነት ሊጠቀሱ የሚችሉ መሆኑን ተገልጧል።

 

በመጨረሻም ቄስ ብርሃኑ ብሥራት ግየሚመሯቸው ግለሰቦች በተከራዩላቸው ጠበቃቸው አማካኝነት ብፁዕ አቡነ እንጦንስ ሊቀ ጳጳስ ወደ ደብረ ጽዮን ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን መጥተው መንፈሳዊ አገልግሎት እንዳይሰጡና በቤተ ክርስቲያኑ ግቢ ውስጥ እንዳይታዩ ለማድረግ የፍርድ ቤት ዕገዳ ለማውጣጥ ከፍተኛ ኢ-ክርስቲያናዊ የሆነ ሙከራ እንዳደረጉ የሀገረ ስብከቱ ጽ/ቤት አታውቋል ።

 

የሀገረ ስበከቱ ሊቀ ጳጳስ አቡነ እንጦንስ ባለባቸው ኃላፊነት ቄስ ብርሃኑ ብሥራትን መክሮ፣ አስተምሮና ገስጾ  ወደ ሕገ ቤተ ክርስቲያን ለመመለስ የተቻላቸውን ሁሉ በማድረግ ሰፊ ጊዜ የወሰደ ተደጋጋሚ ሙከራ ቢያደርጉም ሊመለሱ ባለማቻላቸው የተሰማቸውን ከፈተኛ ሐዘን ገልጸው ከጸለዩ በኃላ የሚከተለውን ውሳኔ እንዳስተላለፉ ተዘግቧል።

 

ከዚህ ሁሉ ጥረት በኋላ ከመጽሐፍ ቅዱስ “ንግራ ለቤተ ክርስትያን” (ማቴ፤ 18፡18) የሚለውን፣ ቀኖና ሐዋርያት አንቀጽ 39፣ ከቃለ ዓዋዲ አንቀጽ 63፤ ቁጥር 2 እና 3 ያሉትን ኃይለ ቃላት በማገናዘብ፤ ይልቁንም ፍትሕ መንፈሳዊ «ካህኑ ኤጴስ ቆጶሱን አልታዘዘው ቢል (ቢንቀው)፣ ብቻውን ቤተ መቅደስ ቢሠራ፤ ኤጴስ ቆጶሱም ሦስት ጊዜ ቢጠራው ትዕዛዙን ተቀብሎ መልስ ባይሰጥ፣ እሱ ከማዕረገ ክህነቱ ይሻር፤ ተከታዮቹም ይሻሩ።» (ፍመ. ምዕራፍ 6፤ አንቀጽ 228፤ 3ኛረስጠብ 22) በማለት የደነገገውን ዋቢ በማደረግ “ቄስ” ብርሃኑ ብሥራት በየትኛውም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን፣ አድባራትና ገዳማት ሁሉ በቅስና የሥልጣነ ክህነት መንፈሳዊ አገልግሉት አንዳይሰጡ ከሥልጣነ ክነታቸው የተሻሩ መሆኑን ገልጸዋል።

 

ብጹዕ ሊቀ ጳጳሱ የጻፉት ደብዳቤ እንደሚያስረዳው ከእንግዲህ “ቄስ” ብርሃኑ ብሥራት እንደተለመደው በማን አለብኝነትና በዕብሪት በስልጣነ ክህነት የሚሰጡት ማንኛውም መንፈሳዊ አገልግሉት በሐዋርያት ትዛዝ “ዘአሰርክሙ በምድር ይኩን እሱረ በሰማያት፤ ወዘፈታሕክሙ በምድር ይኩን ፍቱሐ በሰማያት” መሠረት ሀብተ መንፈስ ቅዱስ የማያሰጥ ሀብተ ስርየት የተለየው የታሰረና የተሻረ መሆኑን አብራርተው፤ “ቄስ” ብርሃኑ ብሥራት ይህን መንፈሳዊ ዳኝነትና ውሳኔ ተቀብለው ተግባራዊ ባያደርጉና በመንፈስ ቅዱስ ሥልጣን ላይ ቢያምጹ በውግዘት ከማኅበረ ቤተ ክርስቲያን ሊለዩ እንደሚችሉ አስጠንቅቀዋል።

 

በመጨረሻም የሰሜን ምዕራብ አውሮፓ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ወደፊት በዚህ ዓይነት የኢትዮጵያ አርቶዶክስ ተዋሕዶ ሕገ ቤተ ክርስቲያንን የሚያፈርስ፤ በቤተ ክርስቲያን ማዕከላዊ አስተዳደር በአመጽ ክንዱን የሚያነሳ፣ በጠቅላላው ከአንዲት ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የአምልኮት አፈጻጸም ሥርዓት እና ቀኖና እንዲሁም ከቃለ አዋዲው መንፈሳዊ የአንድነት መመሪያ ውጭ ሆኖ ለመንቀሳቀስ የሚሞክር ወይም እንዲህ ያለውን ሕገ ወጥ ተግባር የሚያበረታታ፣ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ተባባሪ የሚሆን አገልጋይ ካህን ቢኖርና በበቂ ማስረጃ ከተረጋገጠበት ቤተ ክርስቲያን ልትታገሰው የማትችል መሆኑን በጥብቅ አሳስበዋል።

 

የ“ቄስ” ብርሃኑ ብሥራት ሥልጣነ ክህነት የተሻረበትን ሕጋዊ ደብዳቤ ሙሉ ቃል ከዚህ ቀጥሎ ይመልከቱ።

 

Download (PDF, 1021KB)

 

↧
Viewing all 15006 articles
Browse latest View live