Quantcast
Channel: Ethiopian News | ዘ-ሐበሻ | Latest News Provider | News For All
Viewing all 15006 articles
Browse latest View live

(ሰበር ዜና) መርዝ ተሰጥቷቸዋል የተባሉት የኦሮሚያ ክልል ፕሬዚዳንት ኦቦ ዓለማየሁ አቶምሳ አረፉ

$
0
0

alemayehu and meles
(ዘ-ሐበሻ) መርዝ ተሰጥቷቸው ነው ለዚህ የበቁት የተባሉት የኦሮሚያ ክልል ፕሬዚዳንት ኦቦ ዓለማየሁ አቶምሳ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ።

ለህክምና ብዙ ገንዘብ ወጣባቸው በሚል ሕገወጥ በሆነ መንገድ ከስልጣናቸው እርሳቸው ባላወቁበት በፈቃዳቸው እንደለቀቁ ተደርጎ የተነገረባቸው የኦሮሚያው ክልል ፕረዚዳንት ኦቦ አለማየሁ አቶምሳ በተሰጣቸው የተመረዘ ምግብ ምክንያት የጀመራቸው በሽታ በከፍተኛ ሁኔታ ጸንቶ በተደጋጋሚ በተለያዩ ሃገራት ህክምናቸውን ሲከታተሉ የቆዩ ሲሆን ዛሬ ግን በባንኮክ ታይላድ ለህክምና በሄዱበት ሆስፒታል ሕይወታቸው አልፏል።

በ45 ዓመታቸው በታይላንድ ባንኮክ ሕይወታቸው ያለፈው ኦቦ ዓለማየሁ አቶምሳ በምን ምክንያት የተመረዘ ምግብ እንደተሰጣቸው ባይታወቅም ከርሳቸው ጋር ምግቡን በልቶ የነበረ ግለሰብም እስካሁን በሞት አፋፍ ላይ እንደሚገኝ ለዘ-ሐበሻ የደረሱ መረጃዎች ያመለክታሉ። ለዘ-ሐበሻ ቅርብ የሆኑ የኦነግ የመረጃ ምንጮች “ኦህዴድን የድሮው ኦህዴድ እንዳይሆን ሊያደርጉ የሚችሉ ሰው ስላልነበሩ በሕወሓቶች መርዝ እንዲሰጣቸው ተደርጓል” የሚል አመለካከት ያላቸው መሆኑን ገልጸው ሕወሓት አቶ ዓለማየሁን ቀጠፋቸው ሲሉ ይተቻሉ”፡

ከየካቲት ወር መጀመሪያ ጀምሮ በባንኮክ ህክምና ላይ የከረሙት በምስራቅ ወለጋ ቢሎ ቦሼ ወረዳ ከአባታቸው አቶ አቶምሳ ሚጃ እና ከእናታቸው ወይዘሮ አየለች ብሩ በ1961 ዓ.ም ተወለዱት አቶ ዓለማየሁ አቶምሳ ሕይወታቸው በእንዲህ ያለ ሴራ ማረፉ በኢሕአዴጎች መካከል አለመተማመንን ሊፈጥር እንደሚችል የተለያዩ የፖለቲካ ታዛቢዎች እየገለጹ ነው።
alemayeu-atomsa
የኦህዴድ/ኢህአዴግ ማዕከላዊ ኮሚቴ ፅህፈት ቤት ዛሬ ባወጣው መግለጫ አቶ ዓለማየሁን “ላለፉት 24 ዓመታት የኦሮሞ ህዝብ እና መላው የአገሪቱ ህዝቦች ዛሬ ለደረሱበት የሰላም፣ የዴሞክራሲና የልማት ተጠቃሚነት እንዲበቁ በቁርጠኝነት የታገሉ ነባር ታጋይ ነበሩ” ካለ በኋላ በ1981 ዓመተ ምህረት የደርግን ስርዓት ለመገርሰስ ሲካሄድ የነበረውን የትጥቅ ትግል መቀላቀላቸውን፣ ከ1988 እስከ 1994 ድረስም የኦህዴድ ማዕከላዊ ፅህፈት ቤት እና የድርጅቱ የፖለቲካ ዘርፍ ኃላፊ በመሆን ማገልገላቸውን፣ ከ2002 ዓመተ ምህረት ጀምሮ የኦህዴድ ሊቀመንበር ሆነ ከ2003 ዓ.ም ጀምሮ ደግሞ የኦሮሚያ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ርዕሰ መስተዳድር መሆናቸውን ጠቅሷል። ሆኖም ግን ድርጅቱ እንደተጠበቀው አቶ አለማየሁ በተመረዘ ምግብ መሞታቸውን ከሴራው በስተጀርባ ማን እንዳለ ያስቀመጠው ነገር አለመኖሩን የዘ-ሐበሻ ዘጋቢዎች ጠቁመዋል።

በሌላ በኩል ለዘ-ሐበሻ በደረሱ መረጃዎች ቀጣዩ የኦሮሚያ ክልል ፕሬዚዳንት ወ/ሮ አስቴር ማሞ ይሆናሉ የሚለው ግምት ሚዛን እየደፋ ነው።


በመንግስት ታጣቂው በጥይት ተደብድበው የተገደሉት ባልና ሚስት ፎቶ ተገኘ

$
0
0

Be Hiwehat tataki
እብሪተኛ የመንግስት ታጣቂዎች ለሚቀጥፉት የሰው ህይወት መንግስት ተጠያቂ የሚሆነው መቼ ነው?
ከዳዊት ሰለሞን

የመንግስት ታጣቂዎች በተለያዩ አጋጣሚዎች ደማቸው በትንሽ በትልቁ እየፈላ ሲቪል ዜጎችን የሚጨርሱበት አጋጣሚ ከቀን ቀን እየጨመረ ነው፡፡

የባህር ዳሩን ዘግናኝ እልቂት ለጥቆ ቂርቆስ ቤ/ክ አካባቢ ሁለት ሰዎችን በጥይት በመምታት የወሲብ ደምበኛው እንደነበረች የተነገረላትን ሴት ሲገድል አብሯት የነበረውን ማቁሰሉ አይዘነጋም፡፡የታክሲ ሹፌሩ አልጭንህም ስላለው የታጠቀውን ሽጉጥ በመምዘዝ ለፍቶ አዳሪውን በአጭር አስቀርቶታል፣አራት ኪሎ ቤተ መንግስት አቅራቢያ በሚሄድ መኪና የተርከፈከፈ ጥይት ስንቱን እንዳስቀረ እግዜር ይወቀው ፡፡በየአካባቢው እንዲህ አይነት ዘግናኝ ዜናዎችን መስማት አዲስ አይደለም፡፡

ከትናንት በስቲያ በላፍቶ ክፍለ ከተማ አቦ ማዞሪያ አካባቢ በምስሉ የምትመለከቷቸውን የሶስት ልጆች ወላጆች እብሪተኛው ታጣቂ በጥይት በመደብደብ ገድሏቸዋል፡፡ ግለሰቡ በቁጥጥር ስር ውሏል፡፡እሰየው ነው ፡፡ግን በቃ?እነዚያን ሶስት ህጻናት ማን ነው የሚያሳድጋቸው?ግለሰቡን አምኖ ክላሽ ያስታጠቀው አካል የማይጠየቀውስ እስከመቼ ነው?

መንግስት የመኪና አሽከርካሪዎች የሶስተኛ ወገን ኢንሹራንስ እንዲገቡ እያስገደደ መሆኑ በመኪኖቹ አደጋ ለሚደርስበት ሰው አንዳች ነገር ነውና ይበረታታል፡፡መንግስት በነካ እጁ የሚያስታጥቃቸው ሰዎች ለሚያደርሱት የመብት ጥሰት ኢንሹራንስ ይግባ!!!በእኔ እምነት ስለ ተገደሉት ወላጆችና ወላጅ አልባ ስለሆኑት ልጆች መጮህ የሁላችንም ግዴታ ነው።

[ያ ትውልድ] የኢትዮጵያ ሴቶች፤ የትግል እመቤቶች (ማርች 8 ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን 103ኛ ዓመት ምክንያት በማድረግ)

$
0
0

womens day
ማርች 8 ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን፤ ሴቶች በፆታቸው ምክንያት የሚደርስባቸውን በደል አድልዎና ጭቆና ለማስቀቅ፣ ለማስወገድ ከአደረጉት ትግል ጋር በመያያዝ የሚታሰብ፣ የሚከበር ዓለም አቀፋዊ በዓል ነው። እ.አ.አ በ1911 መከበር የጀመረው ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን ማርች 8 (የካቲት 29 ቀን,
2006 ዓ.ም.) እነሆ 103 ዓመቱ። ዕለቱ ዓለም በማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ መድረኳ ሴቶችን እኩል ታሳትፍ ዘንድ፣ ጾታን መሰረት ያድረጉ መድልዎች ይወገዱ ዘንድ መከበር የጀመረው ዓለም አቀፍ የሴቶችን ቀን ስናከብር ሀገራችን የሴቶችን ጥያቄ መልሳለችን? እንድንዳሥ ግድ ይለናል።

ሙሉውን ለማንበብ እዚህ ይጫኑ

“ኢመማና የካቲት፣ የማህበሩ ውጣውረድ በጨረፍታ”–በስደት የሚገኙ መምህራን አስተባባሪ ኮሚቴ የተሰጠ ወቅታዊ መግለጫ

$
0
0

ethiopian teachers
ጋዜጣዊ መግለጫ፦

ዘመን በመቁጠር ሂደት የወርና የሁኔታ ግጥምጥሞሽ ይከሰታል። በሰነድ የተያዘ ማስረጃ እንደሚያሳየው የካቲት 14 ቀን 1941ዓ.ም “የመምህራን ኅብረት” በደግማዊ ምኒልክ ት/ቤት በአዲስ አበባ ተቋቋመ። የወቅቱ የኅብረቱ ሊቀመንበርም አቶ ሚሊዮን ነቅነቅ ነበሩ። ይህ የመምህራን ኅብረት ስያሜውን እንደያዛ እስከ 1954 ዓ.ም ድረስ ቀጥሏል። ኅብረቱ ከየትኛውም አካል መንግሥትን ጨምሮ አደናቃፊ ኃይል ሳይገጥመው እንዲያውም ድጋፍ እየተደረገለት ነበር እዚህ ወቅት ድረስ የቀየው። ምዝገባ ፣ በሕግ የመታወቅና ያለመታወቅ ጥያቄም አልተነሳም ነበር። ኅብረቱ በ1953 ዓ.ም የዕውቅናና የምዝገባ ጥያቄ ተነስቶ በዚያውም አፈናና የመንግሥት ጣልቃገብነት ተጨምሮበት ጉዞው አስቸጋሪ ሆነ።

ሙሉውን ለማንበብ እዚህ ይጫኑ

አሟሟታቸው “ሆድ ይፍጀው”የተባለው የኦቦ ዓለማየሁ ቀብር ቅዳሜ ይፈጸማል፤ አስቴርና ሙክታር አስከሬኑን ለማምጣት ባንኮክ ናቸው

$
0
0

(ዘ-ሐበሻ) በባንኮክ በህክምና ሲረዱ ቆይተው ያረፉት የኦሮሚያ ክልል ፕሬዚዳንት ኦቦ ዓለማየሁ አቶምሳ የቀብር ስነ ሥርዓት የፊታችን ቅዳሜ በአዲስ አበባ እንደሚፈጸም ታወቀ። አስከሬናቸውን ከባንኮክ ለማምጣትም ወ/ሮ አስቴር ማሞና አቶ ሙክታር ከድር ባንኮክ የገቡ ሲሆን ዛሬ ምሽት 3 ሰዓት ላይ አዲስ አበባ ይገባሉ ተብሎ ይጠበቃል።
alemayeu-atomsa
በ45 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት የተለዩት ኦቦ ዓለማየሁ የክልሉን ፕሬዚዳንትነት ከተቀበሉ በኋላ መርዝ እንደተሰጣቸውና ለበርካታ የአልጋ ቁራኛ እንዲሆኑ አድርጓቸው፤ በህክምና ላይ የሰነበቱ ሲሆን አሟሟታቸውም ሆድ ይፍጀው ሆኗል ይላሉ አስተያየት ሰጪዎች።

የአቶ ዓለማየሁ አቶምሳ የቀብር ስነ ሥርዓት የፊታችን ቅዳሜ በቅድስት ስላሴ ቤ/ክ እንደሚፈጸም የታወቀ ሲሆን አስከሬናቸውን ለማምጣትም በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የመልካም አስተዳደር ሪፎርም ክላስተር አስተባባሪና የሲቪል ሰርቪስ ሚኒስቴር ሚኒስትር የሆኑት ኦቦ ሙክታር ከድር እና የኦሮሚያ ክልል ፕሬዚዳንት ይሆናሉ ተብሎ የሚጠበቀው ወ/ሮ አስቴር ማሞ ባንኮክ ተጉዘዋል። እነዚህ ሁለት ባልስልጣናትም አስከሬኑን ይዘው ዛሬ አዲስ አበባ ይገባሉ ተብሎ ይጠበቃል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ ከባለስልጣኑ ጋር የቀረበ ግንኙነት ነበረን ያሉ ሁለት አስተያየት ሰጪ ጋዜጠኞች በፌስቡክ ገጻቸው ከፕሬዚዳንቱ አሟማት ጀርባ ምስጢር አለ እያሉ ነው። የሁለቱንም አስተያየት ያንብቡት፦

በቅድሚያ የጋዜጠኛ ደመቀ ከበደ አስተያየት

” የ3 ልጆች አባት የነበሩትን አቶ አለማየሁ አቶምሳን የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ሆነው እንደተሾሙ ሰሞን ለዘገባ አጭር ቃለ መጠይቅ አድርጌላቸው ነበር – አዳማ ላይ፡፡ ሰውየው በሙስናና ሙሰኞች ላይ የመረረ አቋማቸውን ሲነግሩኝ ‹‹ቆራጥነት›› ባዘለ ቃና ነበር፡፡
ይህንን በተግባርም አሳይተዋል ብዬ አምናለሁ፡፡
ግን ብዙ ሳይቆዩ መታመማቸው ተሰማ፤ የህመማቸው ምክንያቱ ደግሞ የሌባ ጠላት መሆናቸው ነው ተባለ፡፡ ‹‹ድሮስ አሰለጥ ሌባ መች ለጠላቱ ይተኛል›› … በሚል ነገሩ ወዲህና ወዲያ ተነዛ፡፡ ተጨባጭና ሁነኛ መልስ ግን ያገኘ አላጋጠመኝም፡፡
እንደ ጥላሁንን ገሰሰ ሆድ ይፍጀው ሁላችንም የህመማቸው ምክንያቱን ብንጠብቅም ‹‹በየጊዜው ደም እየቀየሩ ነው ከህመማቸው የሚያገግሙት›› ከሚል ወሬ በቀር ሀቁን ይሄ ነው ያለ የለም፡፡ ከእሳቸው አንደበትም የተሰማ ነገር የለም – እስከማውቀው ድረስ፡፡
ይህ በእንጥልጥል እንዳለ ሰሞኑን ስልጣናቸውን በህመም መልቀቃቸውን ሰምተን ብዙ ሳንቆይ ዛሬ ደግሞ ‹‹ከዚህ ዓለም መለየታቸውን›› አደመጥን፡፡ አቶ ሙክታር ከድርና ወ/ሮ አስቴር ማሞ እየታከሙ ከነበረበት ‹‹ባንኮክ›› ከቤተሰባቸው ጋር ‹‹አስከሬናቸውን›› ሊያመጡ እዚያው መገኘታቸውም ተነግሯል፡፡
ያሳዝናል፡፡ በዚህ ዕድሜ መሞታቸው ብቻ ሳይሆን የአገርን ሙስና ‹‹አፈር ድሜ›› ለማብላት ቁርጠኛነትን ‹‹ለሌሎቹ ሳያሳዩልን›› ሞት ስለቀደማቸው ያሳዝናል፡፡
ከአቶ አለማየሁ አቶምሳ ያጣነው አለ – የሌባ አዳኝ መሆንን!
!”

የሰንደቅ ጋዜጣ አዘጋጅ ፍሬው አበበ በበኩሉ እንዲህ ብሏል፦

“የቀድሞ የኦሮሚያ ክልል ፕሬዚደንት የአቶ አለማየሁ አቶምሳ ዜና ዕረፍት ስሰማ እጅግ አዝኛለሁ፡፡ አቶ አለማየሁን በአካል የማውቃቸው በ2002 ዓ.ም ወሩን በማላስታውሰው ጊዜ ለስራ የቢሮአቸውን ደጃፍ በረገጥኩበት ወቅት ነበር፡፤ ያኔ አቶ አለማየሁ የማስታወቂያ ቢሮ ኃላፊ ነበሩ፡፡ ለቀጠሮ በቢሮአቸው ድንገት ስገኝ ምናልባት ቢያናግሩኝ በሚል ቀቢጸ ተስፋ በመሰነቅ ነበር፡፡ በአጋጣሚ አቶ አለማየሁ በቢሮአቸው ውስጥ ነበሩና እንድገባ ፈቅደውልኝ በጨዋ ደንብ ከመቀመጫቸው ተነስተው በአክብሮት ያደረጉልኝ አቀባበል ምናለ ሌሎቹም ሹማምንት ከሳቸው ቢማሩ የሚያሰኝ ዓይነት ነበር፡፡ ተግባቢ ሰው በመሆናቸው ከሄድኩበት ርዕሰ ጉዳይ ውጪ ስለግሉ ፕሬስ ላይ ላዩን ለመነጋገር ችለናል፡፡ በዚህ አጋጣሚ አቶ አለማየሁ የግሉ ፕሬስ መኖርና መጠናከር ለስርኣቱ ግንባታ ወሳኝ ነው ብለው የሚያምኑ ቀና ሰው መሆናቸውን ለመረዳት ችያለሁ፡፡ በወቅቱ ፍጹም ጤነኛ እና የተረጋጉ፣ ትልቅ የመሪነት ካሪዝማ ያላቸው ሰው እንደሆኑ በአጋጣሚ መታዘብ ችዬ ነበር፡፡
እናም የክልሉ ፕሬዚደንትና የኦህዴድ ሊቀመንበር ሆነው ከተሾሙ ጥቂት ወራት ግዜ በኃላ ከባድ ሕመም ላይ መውደቃቸው በእርግጥም ከጀርባቸው የተሸረበባቸው ተንኮል (ሴራ) ስለመኖሩ በብርቱ እንድንጠረጥር በር የሚከፍት ነው፡፡ ነፍስ ይማር!!”

እውነት እየቆየ መውጣቱ አይቀርም፤ የዘ-ሐበሻ አንባቢዎችስ ምን ትላላችሁ?

ኦኖሌ፡-ሀርከ-ሙራ

$
0
0

እንዲህ ነው በ1860ዎቹ ንጉስ ሚኒሊክ ገና አፄ ሳይባሉ አፄ ቴዎድሮስ ሸዋን ባስገበሩበት ወቅት የተወሰኑ የጎንደሬ ሰራዊት አባላት በሸዋ እንዲቀሩ ተደርጎ ነበር፡፡ እነዚህ የጎንደርና የወሎ ፈረሰኞች ከንጉሥ ሣህለሥላሴ ዘምን ጀምሮ በአርሲና በጨርጨር ሰፍረው ነበር፡፡ አፄ ምኒሊክ ብዙውን ጊዜ በአርሲና በሐረርጌ በማቅናት ዘመቻው በኦሮሞ ላይ ጭፍጨፋ እንደፈፀሙ ተደርጎ ተወርቷል ብዙ ተብሏል፡፡
መራሩ ሀቅ ግን ይህ ነው፡፡

ኦኖሌ፡-ሀርከ-ሙራ

ከማርቆስ ወልደዮሀንስ ዶ/ር
drmarkjohnson@yahoo.com

በአኖሌ የተቆረጠው የማን እጅ ነው? በሂጦሳ አኖሌ የአንድ ኩሩ ኢትዮጵያዊ አርበኛ እጅ ተቆርጧል፡፡ ይህ ሰው ልጅ አበበ ኮላሴ ብሩ ይባላል፡፡ታሪክ ፀሃፊዎቹ ተክለፃዲቅ መኩሪያና ብላቴን ጌታ ኀሩይ ወልደሥላሴ በታሪክ መዛግብቶቻቸው የልጅ አበበን ስም በመጥቀስ የአባታቸውን ስም ለመጥቀስ ያልፈለጉበት ዐብይ ምክንያት ቤተሰቡ በሐረርጌና በሸዋ በነበረው ከፍተኛ ተሰሚነት ነው፡፡ ፊታውራሪ ተክለሃዋሪያት ኃይለሥላሴን ለማንገስ በቅድሚያ የጎንደሬውን ጦር ማሳመን ያስፈልጋል እንዳሉት ለልጅ አበበ አባት ሰም አለመጠቀስ ዋነኛው ምክንያት ፊታውራሪ ኮላሴ ብሩ ይመሩት የነበረው የጎንደሬ ጦር የነበረው ተዳማጭነት እንዲሁም በፍርድ አሰጣጡ ላይ ፍትሐ ነገስቱ በሚያዘው መሰረት ንጉስን ለመግደል መሞከራቸው ይቅርታ የማያሰጥ ወንጀል በመሆኑ ቤተሰቡም እንደዘመኑ ህግ በማመኑ ነው፡፡
anole
በዐፄ ምኒሊክ አጎት በመርዕድ አዝማች ኃይሌ በተጠነሰሰው መፈንቅለ መንግስት ጎንደሬው ደጃዝማች መሸሻ ወርቄን ጨምሮ ከመቅደላው እስር ቤት አፄ ምኒልክን እንዲያመልጡ የረዱ የምኒሊክ ዘመን ታላላቅ ሰዎች ምኒሊክን በመርዕድ አዝማች ኃይሌ ለመተካት የወጠኑት ውጥን ከሸፈ፡፡ ልጅ አበበ ኮላሴ የተመረጠው ለአፄ ምኒልክ ከነበረው ቅርበት የተነሣ ምኒልክን ከደርብ ላይ ገፍትሮ በመጣል ለመግደል ስምምነት አድርጎ ነው፡፡ ልጅ አበበ ኮላሴ የስሜኑ ራስ ውቤ እና የእቴጌ ጣይቱ የስጋ ዘመድ ነበረ ለእቴጌይቱ ከነበረው ቀረቤታና በንጉስ ምኒልክና በእቴጌ ጣይቱ መሃከል በሰተመጨረሻ ጋብቻ እንዲፈጸም ምክንያት የሆኑ የሰሜኑና የሸዋን መሳፍንቶች በማቀራረብ ረገድ ክፈተኛ ሚና የነበራቸው ልጅ አበበ ኮላሴ በእልፈኝ አስከልካይነታቸው ከእራሳቸው የተሻለ ምኒልክን የሚቀርብ ባለመገኘቱ የዐፄ ምኒልክ አጎት በሆኑት በመርእድ አዝማች ኃይሌ አማካኝነት ተመለመሉ፡፡ ልጅ አበበ ኮላሴ ወደ ሸዋ የመጣው ምኒሊክ ገና የሸዋ ንጉስ በነበሩበት በ1860 ዎቹ አጋማሽ ነው፡፡ ከመቅደላው ጦርነት በኋላ አባታቸው ሰራዊታቸውን ይዘው ወደ ምኒልክ በመግባታቸው የጎንደሬ የላስቴ እንዲሁም የሸዋ ሰራዊት እጅግ የተከበረ ነበር፡፡በዚህ ሰራዊት ውስጥ ፊታውራሪ ዋዠቁ እንዲሁም የአቶ አዲሱ ለገሰ አያት ቀኛአዝማች ቀረኩራት ነበሩበት፡፤ ይህ ጦር የጎንደሬ ጦር በመባል የሚታወቅና በሁሉም የኢትዮጵያ ክፍሎች አገርን በማቅናት ረገድ ተወርዋሪ ኃይል የነበረ የሰራዊት ክፍል ነው፡፡

ይህ ታላቅ ሰራዊት በመጀመሪያ በእንጦጦ ቀጥሎም አሁን ግቢ በሚባለው ስፍራ ከከተመ በኋላ ምኒልክ ወደ ተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች በአደረጉት እንቅስቃሴ ከፍተኛና ጉልህ ሚና ተጫውቷል፡፡በእነዚህ የተለያዩ ዘመቻዎች አንቱ የተባለ ክንውን ከፈፀሙ በኋላ ስማቸውን የታሪክ መዝገብ ሳያየው ካለፈ ቤተሰቦች ውስጥ ቤተ-ኮላሴ ወይም ወረ-ኮላሴ የሚባሉት ቤተሰቦች ዋንኞቹ ናቸው፡፡

በሶዶ ፣በቤተ ጉራጌ ፣በአርሲና ባሌ ፣እንዲሁም በሐረርጌ ወደ ማዕከላዊ መንግሰት መምጣት የዚህ ቤተሰብ ሚና ቀላል አልነበረም፡፡ ምስጋና ለፈታውራሪ ተክለሐዋሪያት ኦቶ ባዮግራፊ ወደ አድዋ የዘመተው አብዛኛው የራስ መኮንን ጦር በበላይነት የሚመራው በወንድማማቾቹ በፊታውራ ኮላሴ እና በፊታውራሪ አለሙ የጎንደሬ ሰራዊት መሆኑ በአፅንኦት የተጠቀሰ ቢሆንም ይህንን ታሪክ ፈልፍሎ በማውጣት ረገድ የታሪክ ምሁራኖቹ ከተወሰነ ስፍራ ላይ በመወሰናቸው ዛሬ ኦነግና አህዴድ ለሚያናፋሱት አዳዲስ የፈጠራ ወሬዎች ህዝቡ ሰለባ ሆኗል፡፡በአድዋ ጦርነት የሐረርጌን ሰራዊት አድዋ ድረስ ይዘው በመሄድ የተዋጉት ፊታውራሪ ኮላሴ ብሩና ቤተሰባቸው ወደ አድዋ የዘመቱት ልጃቸው ልጅ አበበ ኮላሴ በምኒሊክ አጎት በተጠነሰሰው የመፈንቅለ መንግስት ሙከራ እጅና እግር ካጡ ከአስራ አምስት ዓመት በኋላ ነው፡፡ የልጅ አበበ እጅና እግር መቆረጥ የፈታውራሪ ኮላሴ ብሩ ና ልጆቻው እንዲሁም ከጎንደርና ላሰታ ተሰባስቦ የተከተላቸውን ሰራዊት በአገሩ ላይ እንዲደራደር አላደረገውም፡፡ በአድዋ ጦርነት በራስ መኮንን መሪነት ታላላቅ ጀብዱዎችን ፈፅመው አገራቸውን ኢትዮጵያን አኩርተዋል፡፡ በአፄ ምኒልክ ይህንን መሰል ቅጣት ለመቀጣት የመጀመሪያው ቤተሰብ ኦሮሞ ወይም ትግሬ ሳይሆን የአማራ ልጅ ነፍጠኛ ነው፡፡ ይህም የተፈፀመው በልጅ አበበ ኮላሴ ላይ ነው፡፡ፊታውራሪ ኮላሴ ብሩ ከእረፍታቸው በኋላ የደጃዝማችነት ማእረግ ተሰጥቷቸዋል፡፡ ደጃዝማች ኮላሴ ብሩ(ሐረርና የአውራጃዋ ግዛት የሚለውን በ1950ዎቹ ይታተም የነበረ መጽሔት) ማየት በቂ ነው፡፡

በልጅ አበበ ኮላሴ ላይ የደረሰውን ቅጣት በአሁን ዘመንና መነፅር አይቶ ምኒልክ ትክክል ሰርተዋል አልሰሩም ለማለት በወቅቱ የነበረውን የዕውቀት የንቃተ ህሊና ደረጃና የፍትህ ስርዓት አንፃር መገምገሙ ተገቢ ነው፡፡ በተመሳሳይ ዘመን በአውሮፓ ጊሎቲን የአንገት መቁረጫ ማሽን ተዘጋጅቶ አንገት የሚቆረጥበት ዘመን ጋር ብናስተያየው በእኛም ሀገር ይፈፀም የነበረው ተመሳሳይ ድርጊት መሆኑን ማስተዋል ይገባል፡፡እንደአጋጣሚ በአኖሌ ጦርነት አልተደረገም፡፡ ጥንትም ይሁን ዛሬ አኖሌ ከተማ ሳትሆን ጥቂት ባለርሰቶች ይኖሩባት የነበረች ጠፍ መሬት ነበረች፡፡ መቶ ሃያም ሆነ መቶ ሰላሳ ዓመት ሩቅ አይደለም፡፡ በጣም ያልራቀ ዘመን በመሆኑም ድርጊቱ የተፈጸመባቸው ቤተ-ኮላሴዎች ጦር ሰብቀው አገር ተሳድበው አልኖሩም፡፡ ስርዓቱን እንዲሁም የኢትዮጵያን ዳር ድንበር በማስከበር ተፋለሙ እንጂ፡- ከእረፍታቸው በኋላ የደጃዝማችነት ማዕረግ የተሰጣቸው የኮላሴ ብሩ ቤተሰቦች ንጉሰ ነገስቱ በጄነቭ የተባበሩት መንግስታት ስብሰባ ሲሄዱ አገሪቱን አደራ ብለው ከተሰናበቷቸው ውስጥ ናቸው፡፡ ፊታውራሪ ጓንጉል ኮላሴ በአኔሌይ ከኢጣሊያ ወታደሮች ጋር ተፋልመው ያገኙትን ውጤት በማድነቅ ወደ ጄኔቫ ያመሩት አፄ ኃይለስላሴ ከስደት መልስ እነዚህን የታሪክ ባለውለታ ቤተሰቦች አላኮሯቸውም ታሪካቸው ደምቆና ጎልቶ እንዲወጣም አላደረጉም፡፡ ይህ ታሪክን አድበስብሶ ማለፍ አዳዲስ የፈጠራ ታሪኮች እንዲፈበረኩና በዚህም ብዙዎች ዕዳ ከፋይ የሆኑበት ሁኔታ ታይቷል፡፡የምጣዱ ሳለ የዕንቅቡ ተንጣጣ እንዲሉ እጅና እግር የገበረው የአማራ ብሔር ነፍጠኛው ሆኖ ሳለ በኢትዮጵያ የጦርነት ታሪክ ታይቶም ሆነ ተሰምቶ የማይታወቅ የክርስቲያን ጦር ጡት ቆረጠ የሚል ማስረጃ የማይቀርብበት የሐሰት ታሪክ ትንታኔዎችን በማቅረብ በተራ አሉባልታና በሬ ወለደ የፈጠራ ታሪክ ሕዝብን መንዳት መሞከር ታላቅ ወንጀል ነው፡፡ታቦት ይዞ የሚዘምት ሰራዊት ሴትን በጥፊ መምታት እንኳን እንደወንጀል የሚመለከት ማህበረሰብ ምን ለማግኘት ምን ለማትረፍ የሴት ጡት ይቆርጣል፡፡ የአበበ ኮላሴን እጅና እግር መቆረጥና መቀጣት እንዲሁም የኤርትራ ባንዳ ሰራዊትን እጅና እግር መቆረጥ የተረኩ የታሪክ ጸሐፍት ማንን ፈርተው ለምን ብለው ይህንን ታሪክ ሳይዘግቡት ቀሩ ቢባል፡ መልሱ ድርጊቱ ፈጽሞ ያልተካሄደ በመሆኑ ብቻ ነው፡፡በጣም የሚያኮራውና የሚያስደስተው ቤተ-ኮላሴዎች የፖለቲካ ትርፍም ሆነ ሌላ ነገር ለማግኘት በየትኛውም ስርዓትም ሆነ ዘመን ይህንን ታሪክ አጉልተው አልተናገሩም አልዋሹም አልቀጠፉም፡፡ኢትዮጵያን ግን ጠበቁ፡፡ ሞቱላት ደሙላት፡፡ይህ ታሪክ የኦህዴድ ታሪክ የኦነግ ታሪክ ቢሆን ስንት ዘርፍና ቅጥያ ወጥቶለት ሌላ ሃውልት በቆመ ነበር፡፡ይህ ታሪክ የአንድ ኩሩ ኢትዮጵያዊ ቤተሰብ ታሪክ ነው፡፡

ልጅ አበበ የተቀጣበት ስፍራ የአሁኗ አኖሌ ነበረች፡ በስፍራው የነበሩ ሰዎች ልጅ አበበ ኮላሴን በኦሮሚኛ ሃርከ ሙራ -እጀ ቆራጣ ለማለት የሰጡት ስም ዛሬ ከበሮ እየተደለቀበት ያለ በተለይም ድህረ ኢህአዴግ ሀርመ ሙራ የምትል ቅጥያ የኦነግና የኦህዴድ ካድሬዎች በማከላቸው ጡት ጭምር ተቆርጧል አስብሎ በሀሰት የፖለቲካ ትርፍ ፕሮፓጋንዳና ሃውልት በመስራት በሚለዮኞች የሚቆጠር ብር ቢዝነስ በሚያጧጡፉ ግለሰቦች ሀሰት እውነት ተደርጎ መዘገቡ አሳፋሪ ነው፡፡ እውነት ነው የልጅ አበበ ኮላሴ ቀኝ እጅና ግራ እግር የተቆረጠው በንጉሳዊ ትእዛዝ ነው ፈፃሚዎቹም ከአሁኗ እንጦጦ ወደ አርሲ ሄደው የሰፈሩት ወረ-ሂጦመሌ በሚባል የሚታወቁት የኦሮሞ ጎሳዎች ነው፡፡ የተገላቢጦሽ እንዲሉ በፈሰሰው የነፍጠኛው የልጅ አበበ ኮላሴ ደም ዛሬ ከፍተኛ የፖለቲካ ትርፍ ለማትረፍ የሚንቀሳቀሱ ዋሾዎችን ማየት አሳፋሪ ከመሆኑም በላይ መንግስት ጉዳዩን በዝምታ መመልከቱ አሳሳቢም ጭምር ነው፡፡መንግስት በዚህ ሃውልት መቆም አምንበታለሁ ካለም በበደኖ በአሶሳ በአርሲ ነገሌ በአርባጉጉ በጂማ አንገታቸው ለተቀላ ደማቸው እንደጅረት ለፈሰሰ ሰማዕታት ሃውልት የማቆም ግዴታ ይኖርበታል፡፡
የፊታውራሪ ኮላሴ ቤተሰቦች በሁለተኛው የኢትዮ ኢጣሊያ ወረራ ወቅትም ከፍተኛ ተጋድሎ አድርገዋል፡፡

ፊታውራሪ ጓንጉል ኮላሴና ወንድማቸው ኃይለማሪያም ኮላሴ በኢትዮጵያ ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ ታንክ የማረኩ መሆናቸውን ጳውሎስ ኞኞ አልተወራላቸውም እንጂ በማለት በኢትዮጵያና በኢጣሊያ ጦርነት ወቅት ስለፈፀሙት ተጋድሎ በመጽሐፉ ዘግቧል፡
ሻምበል መብራቴ ኮላሴ የጥቁር አንበሳ ሰራዊት አባል ማይጨው በጀግንነት ወድቀዋል ተክለፃዲቅ መኩሪያ ዘግበውታል

የይፍቱ ስራ ኮላሴ ልጅ ፊታውራሪ ነገደ ዘገየ በጎንደርና በሐረር ከኢጣሊያ ጋር በመዋጋት ከፍተኛ ተጋድሎ ፈጽመዋል፡፡ ልጅ አበበ ኮላሴ በፈጸሙት ስህትት ተቀጥተዋል፡፡ እጅና እግራቸው ከተቆረጠበት አርሲ አኖሌ በተቆረጠ እጃቸው አንበሳ ገድለው ለአፄ ምኒልክ የአንበሳ ጎፈር ልከዋል፡፡ ምኒልክም የእጄን በእጄ በማለት መፀፀታቸው አሁን ድረስ የሚወራ ታሪክ ነው፡፡ እናም በአማራው ላይ ለተፈፀመው ድርጊት በኦሮሞ ላይ እንደተፈፀመ ተደርጎ በፈጠራ ድርሳን የሚወራው ወሬና ሕዝብን ከሕዝብ የማለያየት እንቅስቃሴ በአስቸኳይ መቆም አለበት፡፡

በፓርስ ኢትዮጵያዊው ከጎዳና ተዳዳሪነት ያወጡትን እናትና ልጅ ገድሎ ተሰወረ!

$
0
0

ዘጋቢ፦ክንፉ አሰፋ (ጋዜጠኛ)

እናትና ህጻን ልጅዋን ገድሎ የተሰወረው ሰውዬ ትውልዱ ኢትዮጵያዊ ሲሆን በፈረንሳይ ፓሪስ ክርተማ የጎዳና ላይ ተዳዳሪ ነበር:: ሟች ወ/ሮ ክውን ገዳሙ ትባላለች:: ከቤትዋ ወደ ስራ ቦታ ሲመላለሱ ተጠርጣሪውን የዩታል:: በጎዳናው የተጎሳቆለውን ሰው(ጉዳዩ በህግ ስለተያዘ ስሙን እዚህ ላይ አንጠቅሰውም) ስለሚያሳዝናቸው ባለፉ ባገደሙ ቁጥር እጃቸውን ይዘረጉለት ነበር::

ከግዜ በኋላ ከክረምቱ ብርድ እንዲገላገል ሲሉ ይህንን የጎዳና ተዳዳሪ ለግዜው በቤታቸው አስጠጉት:: የአቅማቸውን እየረዱት አብረው ለወራት ኖሩ::

ባለፈው ሳምንት አንድ አስደንጋጭ ክስተት በቤተሰቡ ውስጥ ተፈጸመ:: በችግሩ ያስጠጉት ሰው ከተኙበት በጭካኔ ገድሏቸው አመለጠ::

ወ/ሮ ክውን ገዳሙ የሶስት ልጆች እናት ሲሆኑ በፈረንሳይ ፓሪስ ለረጅም ግዜ ኖረዋል:: የሶስት ልጆች እናትም ናቸው:: ያለአባት ከሚያሳድጓቸውን ሶስት ልጆች ውስጥ አንደኛዋና የሁሉም ታናሽ ከሆነችው ጋር ላይመለሱ ይህችን አለም ባለፈው ሳምንት ተሰናበቱ::

ገዳዩ ጭካኔ በተሞላበት መንገድ በጩቤ ሰነጣትቆ ነው እናትና ልጅን ለህልፈት የዳረገው- እንደ ፈረንሳይ የዜና ምንጭ:: ባጎረሱት እጅ ተነከሱ:: ደግ ባደረጉ ምላሹ ግድያ ሆነ: ለዚያውም አረመኔያዊ ግድያ::

ነብሰ ገዳዩ ለግዜው ተሰውሯል:: የፈረንሳይ ፖሊስ ከኢንተርፖል ጋር በመሆን ጉዳዩን በጥብቅ ይዞታል:: እኛም እየተከታተልን ጉዳዩ ምን እንደደረሰ እናቀርብላችኋላን::

በካናዳ ለምትኖሩ ኢትዮጵያውያን እና የኢትዮጵያውያን ወዳጆች ጥሪ


አንድነት በ17 ከተሞች ሕዝባዊ ንቅናቄ ሊያደርግ ነው

$
0
0

bahr dar 19
አንድነት ፓርቲ ሁለተኛውን ዙር የሚሊኖች ድምፅለነፃነት ህዝባዊ ንቅናቄ ይፋ ማድረጉን አስታወቀ። ህዝባዊ ንቅናቄው የሚካሄድባቸው 17 ከተሞችም ተለይተው ታውቀዋል።

የድርጅቱ ልሳን ይፋ እንዳደረገው አንድነት ለዲሞክራሰና ለፍትህ ፓርቲ ዛሬ ይፋ ያደረገው የህዝባዊ ንቅናቄ መርሃግብር በተከታታይ ሊካሂዳቸው ካቀዳቸው ህዝባዊ ንቅናቄዎች መካከል አንዱ በየሆነውን የሚሊዮኖች ድምፅ ለመሬት ባቤትነት(Millions of voices for land ownership) የሚል ስያሜ የሰጠውን የህዝባዊ ንቅናቄ ነው፡፡ መረሃ ግብር በዛሬው እለት ይፋ የተደረገው ቀበና መድኃኔዓለም ቤ/ክ ፊተ ለፊት በሚገኘው የፓርቲው ጽ/ቤት ነው፡፡ ህዝባዊ ንቅናቄው ይፋ በተደረገበት መግለጫ ላይ አንድነት የመሬትን ጉዳይ በአጀንዳነት በመምረጥ ህዝባዊ ንቅናቄ ለማድረግ የመረጠባቸው ምክንያቶች በዝርዝር ቀርበዋል፡፡

በአዲስ አበባ በሚደረግ ትዕይንተ ህዝብ እንደሚጀመር የሚጠበቀው “የሚሊዮኖች ድምፅ ለመሬት ባቤትነት” ህዝባዊ ንቅናቅ 14 ከተሞች ላይ ሰላማዊ ሰልፍ እንደሚደረግና ሶስት ከተሞችም በተጓዳኝ ለህዝባዊ ንቅናቄው መመረጣቸው ታውቋል፡፡ ንቅናቄው የሚካሄድባቸው ከተሞች አዲስ አበባ ፣ደሴ ፣ሐዋሳ ፣አዳማ/ናዝሬት ፣መቀሌ ፣ደብረታቦር ፣ ደብረ ማርቆስ ፣ድሬ ደዋ፣ ጅንካ፣ ቁጫ፣ አሶሳ፣ነቀምት፣ለገጣፎ፣አዲስ አበባ ሲሆኑ ተጓዳኝ ከተሞቹ ወልዲያ፣ ጋምቤላ፣ ም/አርማጨሆ(አብርሃ ጅራ) እንደሆኑ ለማወቅ ተችሏል፡፡

አንድነት ፓርቲ ባለፈው ዓመት(2005ዓ.ም) ለሶስት ወራት “የሚሊዮኖች ድምፅ ለነፃነት” በሚል መሪ ቃል ህዝባዊ ንቅናቄ ማድረጉ የሚታወስ ነው።

Hiber Radio: የኢትዮጵያው አገዛዝ ሮኬትን ጨምሮ ከኤርትራ በየመን በኩል ሊገባ ነበር ያለውን መሳሪያ ያዝኩ አለ

$
0
0

የህብር ሬዲዮ የካቲት 30 ቀን 2006 ፕሮግራም

እንኳን ለዓለም አቀፉ የሴቶች ቀን አደረሳችሁ

ጋዜጠኛ ሃብታሙ አሰፋ

ጋዜጠኛ ሃብታሙ አሰፋ

<... ...>>

አቶ ወረታው ዋሴ የሰማያዊ ፓርቲ የፋይናንስ ጉዳይ ሀላፊ በአደባባይ ተቃውሟቸውን ያሰሙትን የፓርቲው አባላትን አስመልክቶ ከሰጡት ቃለ ምልልስ (ሙሉውን ያዳምጡ)

>

አቶ ጌታነህ ካሳሁን የሰማያዊ ፓርቲ የሰሜን አሜሪካ የድጋፍ ኮሚቴ ሰብሳቢ ለህብር ከሰጡት አስተያየት (ሙሉውን ያዳምጡት)

<...>

ዶ/ር ታዬ ዘገዬ የኢትዮጵያ ሕዝብ የጋራ ትግል ሸንጎ የወቅቱ ሊቀመንበር ለሱዳን ድንበር እንዳይሰጥ ስለሚያደርጉት እንቅስቃሴ ለህብር ከሰጡት ቃለ ምልልስ የተወሰደ(ሙሉውን ያዳምጡት)

የዓለም አቀፍ የሴቶች ቀንና በመከራና በመብት ረገጣ ውስጥ ያሉ የኢትዮጵያውያን ሴቶች ህይወት(ልዩ ዘገባ)

የአሜሪካ መንግስት በ2013 የኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብት አያያዝን አስመልክቶ ያወጣው ሪፖርት ሲቃኝ

ኢትዮጵያ በዚህ አገዛዝ እየደማች እየተመዘበረች ነው። ይሄ ውድቀት ነው…>> ዶ/ር አክሎግ ቢራራ ከህብር ጋር ካደረጉት ቆይታ (ሁለተኛ ክፍል ቃለ መጠይቅ)

የህብር ሬዲዮ አራተኛ ዓመት በዓል ልዩ ሪፖርት

ሌሎችም ዝግጅቶች

ዜናዎቻችን

- የኢትዮጵያው አገዛዝ ሮኬትን ጨምሮ ከኤርትራ በየመን በኩል ሊገባ ነበር ያለውን መሳሪያ ያዝኩ አለ

- የግብጽ የቀድሞ ጄኔራል ከህዳሴ ግድብ ካልተጠቀምን አባይ ግርጌ መሞት አለብን አሉ

- ለሩጫ ወጥተው ተቃውሟቸውን ስላሰሙ የታፈኑት የሰማያዊ ፓርቲ አባላት የካ ፖሊስ መምሪያ በእስር ላይ ናቸው

- ከኢትዮጵያ የእርስ በእርስ ጦርነት ያመለጡት ኢትዮጵያዊው የቀዶ ጥገና ባለሙያ በቬጋስ የበርካቶችን ሕይወት እየታደጉ ነው

- አብርሃ ደስታ ሕወሓት ለአለማየሁ አቶምሳ ሐዘን ለሶስት ቀን ባንዲራ ዝቅ ስላደረገ የኦሮሞን ሕዝብ ለማክበር አድርጎ ማቅረቡን አጣጣለ

ሌሎችም ዜናዎች አሉ

ኢህአዴግ ዳግም በክፍፍል ጎዳና?… (ከተመስገን ደሳለኝ)

$
0
0

ከተመስገን ደሳለኝ

ከዚህ ቀደም በተለያየ ጊዜ በተዘጋጁ ሁለት ፅሁፎች፣ የድህረ መለስን ኢህአዴግ የኃይል አሰላለፍ ለማመልከት መሞከሬ የሚታወስ ቢሆንም፤ ዛሬም ያልተጠበቁ ክስተቶችን ማስተዋላችን አልቀረም፡፡ በርግጥ «አዲሱ የኢህአዴግ አሰላለፍ ፪» በሚል ርዕስ ቀርቦ በነበረው ተጠየቅ ከሞላ ጎደል ሀገሪቷን እንደንጉስ ሚካኤል ከጀርባ ሆነው የሚያሽከረክሯት ህወሓት እና ብአዴን መሆናቸው የተጠቀሰበት አውድ ብዙም አልተቀየረም፡፡ ይሁንና በኦህዴድ እና ደኢህዴን ውስጥ እየታየ ያለው የእርስ በእርስ መተጋገል መደምደሚያ ምናልባት ወቅታዊውን መልከአ ኢህአዴግ ሊለውጠው የሚችልበት አጋጣሚ እንዳለ እገምታለሁ፤ ማን ያውቃል? …እነዚህን ኩነቶች ታሳቢ አድርገን የገዢው ፓርቲ አክራሞትን በአዲስ መስመር ጨርፎ ወደመመልከቱ እንለፍ፡፡

የደቡብ ኢትዮጵያ «ብላቴኖች»

ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ

ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ

ክልሉን የሚያስተዳድረው የደኢህዴን የአመራር አባላት በስርዓቱ ልሂቃን የፖለቲካ ግምገማ ገና «ብላቴና» ተደርገው የሚወሰዱበት የትምክህት ዘመን አላከተመም፡፡ በርግጥ ድርጅቱ ደርግን ለመጣል በተደረገው የትጥቅ ትግል ላይ የተሳተፈ ባለመሆኑ፣ ዛሬም ፖለቲካን (ሀገር ማስተዳደርን) በበረሃው ትግል ተፈትኖ ከማለፍ ጋር ከሚያጋምዱት የግንባሩ ጉምቱ መሪዎች ዘንድ፣ ይህን መሰል ማጣጣያ የሚጠበቅ ነው፡፡ ከዚህ በተጨማሪ ለደኢህዴን ደካማነት በምክንያትነት የሚነሳው ጉዳይ ከአወቃቀሩ ጋር የሚያያዝ ነው፤ ይኸውም በክልሉ የሚገኙ 56 የተለያዩ ዘውጎችን ማቀፉ ለመከፋፈል አደጋ በቀላሉ የሚጋለጥበትን ዕድል የማስፋቱ እውነታ ነው፡፡ ይህም ሆኖ ከክልሉ ነዋሪዎች በቁጥር የሚልቁት የወላይታና የሲዳማ ተወላጆች፣ በደኢህዴን ውስጥ ያላቸው ተሰሚነት (ተፅዕኖ) የገዘፈ መሆኑን ለመረዳት፣ ሕገ-መንግስቱ ከፀደቀበት ጊዜ ጀምሮ የፓርቲውን ሊቀ-መንበርነትም ሆነ የክልሉ ፕሬዚዳንትነት ከሁለቱ ብሔሮች በቀር፣ ለሌሎቹ የሰማይ ያህል የራቀ ያደረገውን «ዲሞክራሲያዊ ማዕከላዊነት» መጥቀሱ በቂ ነው፡፡

ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ደግሞ የፓርቲው ሊቀ-መንበር ኃይለማርያም ደሳለኝ የያዘውን መንግስታዊ ስልጣን የሚመጥን ተሰሚነት ለማግኘት ድርጅታዊ ድጋፍ ማሰባሰብ ላይ ያተኮሩ የሚመስሉ ክስተቶችን ሲከውን ታዘብናል፡፡ ኩነቱን በስነ-አመክንዮ ለማጠናከር ጥቂት ማሳያዎችን ላቅርብ፡- በጠቅላይ ሚኒስትርነት መንበር ላይ ከተቀመጠ በኋላ፣ በደኢህዴን ውስጥ ያሉ የተወሰኑ ተገዳዳሪዎቹን ከኃላፊነታቸው ከማንሳትም አልፎ፣ ደጋፊዎቹ (ታማኞቹ) እንደሆኑ የሚነገርላቸውን በከፍተኛ ሥልጣን ላይ አስቀምጧል የሚያስብለው፣ ከወራት በፊት በፓርቲውም ሆነ በደቡብ ክልል ከእርሱም የበለጠ ተሰሚነት የነበረውን ሽፈራው ሽጉጤን አንስቶ፤ ትጉህ አገልጋዩ እንደሆነ የሚነገርለትን ደሴ ዳልጌን ተክቶታል፤ በቅርቡ ደግሞ ሌላኛው ‹የደኢህዴን ቁልፍ ሰው› የሚባለው የፖለቲካ (የድርጅት) ጉዳይ ኃላፊ እና የክልሉ ምክትል ፕሬዚዳንት አለማየሁ አሰፋን ያለአንዳች ኮሽታ «በትምህርት ስም» ከቦታው አንስቶታል (ይህ ጉዳይ እስከአሁን ድረስ መንግስታዊው ሚዲያ የዜና ሽፋን አላገኘም)፡፡ በግልባጩ ታማኝነታቸውን ያስመሰከሩ፣ ከሲዳማ ብሔር ውጪ ያሉ ጓዶቹን በፌደራል መንግስቱ ወሳኝ የስልጣን እርከኖች ላይ አስቀምጧል፡፡ ለማሳያ ያህልም አሰፋ አብዩ /ሀድያ/፣ ወርቅነህ ገበየውን ተክቶ የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽነር፤ ደበበ አበራ /ከፋ/፣ የኢህአዴግ ዋና ጽህፈት ቤት ኃላፊ፤ ውዱ ሀቶ /ሸካ/፣ የፀረ ሙስና ምክትል ኮሚሽነር፤ አማኒኤል አብርሃም /ወላይታ/፣ በሚኒስቴር ዴኤታ ማዕረግ የጠቅላይ ሚኒስትሩ የሕዝብ አደረጃጀት አማካሪ፤ ሰለሞን ተስፋዬ /ጉራጌ/፣ በተመሳሳይ ማዕረግ የፕሬስ አማካሪ፤ ካይዛ ኬ (ጂንካ) በገቢዎች ባለስልጣን የገብረሀዋድን ቦታ ተክቶ የገባ እና የፌደራል ዋና ኦዲት መስሪያ ቤት ምክትል ኃላፊ ተደርጋ የተሾመችውን የወላይታዋ ተወላጅን መጥቀስ ይቻላል (ከደኢህዴን የሥራ-አስፈፃሚ አባላት መካከል የኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት ሚኒስትሩ ሬድዋን ሁሴን እና መከላከያ ሚኒስትሩ ሲራጅ ፈጌሳም የሲዳማ ተወላጅ አለመሆናቸውን ልብ ይሏል) ይህንን ጉዳይ እንዲህ በብሔር ደረጃ ቁልቁል አውርደን እንድንመለከተው የሚያስገድደን ስርዓቱ ከሚያራምደው የፖለቲካ ፍልስፍና እና በክልሉ እየተነሱ ካሉ የማንነት ጥያቄዎች ጋር የመቆራኘቱ አንድምታ ነው፡፡ በተለይ

ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ሲዳማዎች ራሳቸውን ችለው

በክልል ደረጃ ለመዋቀር ተደጋጋሚ ጥያቄ አቅርበው አያሌ መስዋዕትነትን መክፈላቸው ይታወሳል (በኢህአዴጋዊ የክልል አሰያየም ቀመር ሕገ-መንግስታዊ ድጋፍ ያላቸው መሆኑ ሳይዘነጋ)፡፡ ይሁንና ጥያቄው ተቀባይነት ቢያገኝ የክልሉ አስተዳደር መቀመጫ የሆነችውን አዋሳን ከመውሰዳቸውም በላይ፣ ሊያስከትል የሚችለው አለመረጋጋት ሲታከልበት፣ ህዳጣን ልሂቃኑን የኢኮኖሚ ጥቅመኝነት ያሳጣቸዋል፡፡ ይህ ስጋትም በደኢህዴን ውስጥ ከሲዳማ ተወላጆች ውጪ ካሉ የአመራር አባላት ድርጅታዊ ድጋፍ ለማግኘት ብርቱ ትግል ከሚያደርገው ኃይለማሪያም ደሳለኝ ጋር በወሳኝ ሰዓት፣ መሀል መንገድ ላይ ቢያስተቃቅፋቸው የማይታመን አይሆንም፡፡

eprdfየእነዚህ አዳዲስ ኩነቶች (ሹም ሽሮች) መግፍኤ፣ በሁለት የቢሆን ሃሳቦች ተነጣጥለው ሊታዩ ይችላሉ፡፡ የመጀመሪያው ኃይለማሪያም ደሳለኝ የጠቅላይ ሚንስትርነት ሹመቱን ተከትሎ ‹በዚህ ላይ ፈርም›፣ ‹ይህንን ተናገር›፣ ‹እንዲህ አይነት አስተያየት ስጥ!!› ወዘተ የሚሉ ከጀርባ ሆነው የሚሾፍሩት የአለቆቹ ቀጭን ትዕዛዛትን የሚገዳደርበት ፖለቲካዊ ጉልበት ለማሰባሰብ እና በቁርጥራጭ ጨርቅ በተጣጣፈው እናት ድርጅቱ ውስጥ ያሉ ችግሮችን ስልታዊ በሆነ መልኩ አስወግዶ ቅቡልነቱን ለማጠናከር እንቅስቃሴ ጀምሯል የሚል ሊሆን ይችላል፡፡
ሌላኛው ደግሞ ከኢትዮጵያውያንም አልፎ በውጪ ዜጎች ሳይቀር ‹ጠቅላይ ሚኒስትሩ አሻንጉሊት ነው› የሚለውን እምነት ለማስቀየር በህወሓትና ብአዴን እየተደረገ ያለ ፖለቲካዊ ጨዋታ ሊሆን የመቻሉ ጉዳይ ነው፡፡

ኦህዴድ

ባለፉት የህወሓትም ሆነ የአቶ መለስ ዜናዊ የበላይነት በገነኑባቸው ዘመናት፣ ኦህዴድ ምንም እንኳን ስርዓቱን ካነበሩ የግንባሩ አባል ድርጅቶች አንዱ መሆኑ ባይካድም፣ በስጋት መታየቱ የአደባባይ እውነታ ነው፡፡ እንዲያውም በአንድ ወቅት አቶ መለስ ራሱ «ኦህዴድ ሲፋቅ ኦነግ ነው» ማለቱ አይዘነጋም፡፡ ከሶስት ያላነሱ የስራ አስፈጻሚ አባላቱ፣ ድርጅቱን ከድተው ኦነግን መቀላቀላቸውም የውንጀላው ማሳያ ተደርጎ እስከመወሰድ ደርሶ ነበር፡፡ ይህ ሁኔታም ኦህዴድን የተረጋጋ አመራር እንዳይኖረው ከማደናቀፉም ባሻገር፣ በተቀነባበረ ማኪያቬሊያዊ ሴራ እርስ በርስ በማይተማመኑና በተከፋፈሉ ሰዎች ስር እንዲቆይ አስገድዶታል፡፡ ግና፣ ኩነቱን ምፀት የሚያደርገው ህወሓት በረሃ እያለ ያሳትመው በነበረው ልሳኑ «የኦሮሞ ጥያቄና የኢትዮጵያ አብዮት» በሚል ርዕስ ባሰራጨው ፅሁፍ ኢህአፓን «የኦሮሞ ሕዝብ በነፍጠኛው ላይ የነበረውን ተገቢ ጥላቻ በማራገብ ፋንታ ለማብረድ በተጨባጭ ተንቀሳቅሷል» («የትግል ጥሪ» 3ኛ ዓመት ቁጥር 10፣ 1979 ዓ.ም) ሲል ይከስሰው እንደነበረ ማስተዋላችን ነው፡፡

በአናቱም አቶ መለስ እስከ ህልፈቱ ድረስ በኦህዴድ ደስተኛ እንዳልነበረ ይነገራል፡፡ ይህ ግን ‹የኦሮሞን ሕዝብ በአግባቡ አላገለገለም› ከሚል ቁርቆራ የተነሳ አይደለም፤ እንዲህ አይነቱ ስሜት ሌላውን ክልል ቀርቶ ትግራይንም የሚመለከት ቢሆን አሳስቦት አያውቅምና፡፡ የእርሱ ቅሬታ ‹ህዝቡን አሳምነውም ሆነ ጠርንፈው ከድርጅቱ ጎን አላሰለፉትም›፣ ‹ሁላችንንም በሚያሳጣ መልኩ ዘረፋ ውስጥ ገብተዋል›፣ ‹ዲሲፕሊን የላቸውም…› የሚሉና ሌሎች መሰል መነሾዎች ናቸው፡፡ እንዲህ ያለ የድርጅቱ «እንዝህላልነት» ደግሞ የህዝቡ ልብ ይበልጥ ኦነግን እንዲናፍቅ ማስገደዱን መለስ ዜናዊ ጠንቅቆ ያውቅ ነበር፡፡ ለዚህም ይመስለኛል የክልሉን ባለስልጣናት ሁሉ ወደ ጎን ብሎ እታች ድረስ በመውረድ የወረዳ አመራሮችን ቀጥታ ያለ ሥልጣን ተዋረድ በስልክ እስከማናገር የተገደደባቸው ቀናት የበዙት፡፡ በርግጥ በድርጅቱ ስብሰባዎች ላይ መተላለፍ ያለባቸውን ውሳኔዎች በፅሁፍ መስጠት እና ለአመራርነት የሚመረጡ ሰዎችን መመደብ ድረስ ባሉ ጉዳዮች ጣልቃ የመግባቱ ነገር ማንም አሌ የማይለው በግልፅ ይታይ የነበረ ክስተት ነው፡፡

የሆነው ሆኖ ከምንጮቼ እንዳረጋገጥኩት አባዱላ ገመዳ ዕድሜውን ሙሉ ሲፈራ የኖረው መለስ ዜናዊን ብቻ ነበር፤ መለስ ደግሞ ይህችን ምድር ለመጨረሻ ጊዜ ከተሰናበታት አንስቶ የተቆጠሩት በርካታ ወራት ፍርሃቱን ጥሎ ነፃነቱን እንዲጎናፀፍ ለመርዳት ያስችሉታል ብዬ አስባለሁ፡፡ እናም በዚህ መልኩ ተፈጥሮ ያመቻቸለትን ታሪካዊ አጋጣሚ ተጠቅሞ ይደቆስ የነበረውን ኦህዴድ ከወደቀበት ለማንሳት ሙከራዎችን እያደረገ ይመስለኛል፡፡ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ኦህዴድ በሚያደርጋቸው ስብሰባዎች ላይ የሚቀርቡ አንዳንድ አጀንዳዎችና አቋሞችን የአባዱላ ግፊት እንዳለባቸው ስናስተውል፣ «ጄነራሉ» ወሳኝ ሰው ለመሆን እያደረገ ያለው የጥንጣን ጉዞ ምን ያህል እየሰመረለት እንደሆነ ለመረዳት ያስችላል፡፡ ይህንን መከራከሪያ ከለጠጥነው ደግሞ፣ ከህወሓት/ብአዴን ጋር ትከሻ መገፋፋት ጀምሯል ወደሚል ጠርዝ ይገፋናል፡፡ ይህም ባይሆን እንኳ ከኃይለማርያም ደሳለኝ የተሻለ ተሰሚነት እንዳለው ለመናገር የሚያስደፍሩ ማስረገጫዎች አሉ፡፡ ጠቅላይ ሚንስትሩ ቀን የከዳ ዕለት በተናጠል በኃላፊነት ሊያስጠይቁት የሚችሉ ጉዳዮችን ሳይቀር፣ በያዘው ሕገ-መንግስታዊ ሥልጣን ከመወሰን ይልቅ በቡድን እንዲያልቅ ሲስማማ፤ በግልባጩ አፈ-ጉባኤው ከዚህ ቀደም በምክር ቤቱ ውስጥ ተነስተው ለአቶ መለስ ይቀርቡ የነበሩ ጉዳዮችን ወዲያውኑ መፍትሔ እንዲያገኙ በማድረግ ሲቋጫቸው ተደጋግሞ ተስተውሏል፡፡ ኦህዴድንም በሚመለከት ‹በድርጅታዊ መደጋገፍ› ስም ማንም ጣልቃ መግባት እንደማይችል በይፋ እስከ መናገር መድረሱን ምንጮች ጠቅሰውልኛል፡፡ በቀጣይ አመት የሚደረገውን አምስተኛ ዙር አገር አቀፍ ምርጫን አስመልክቶም እየተደረገ ባለው ዝግጅት በሃሳብ አመንጭነት እየተሳተፈ ነው፡፡ ከጥቂት ወራት በፊት ለምክር ቤቱ የቋሚ ኮሚቴ አባላት፣ ከሁሉም የመንግስት መስሪያ ቤት ለተወከሉ እና ምርጫ ቦርድ ሀላፊዎች /ፕሮፌሰር መርጋ በቃና እና ዶ/ር አዲሱ ገ/እግዚአብሔር በተገኙበት/ «የአውራ ፓርቲ ዴሞክራሲያዊ ባህሪያት» በሚል ርዕስ ጥናታዊ ፅሁፍ ማቅረቡ አስረጅ ሆኖ ሊወሰድ ይችላል (በነገራችን ላይ ስርዓቱ በምርጫ ስም የሚፈፅመውን ደባ ፍንትው አድርጎ የሚያሳየው፣ ሁለቱ የቦርዱ ኃላፊዎች የዚህ አይነቱ ውይይት ላይ ተሳታፊ መሆናቸው ነው)፡፡ እንዲሁም ይህንኑ ጉዳይ በተመለከተ በአዳማ ለክልል አፈ-ጉባኤዎች ሰፊ ትንተና ሰጥቷል፡፡

የአባዱላ ገመዳንና የበረከት ስምኦንን መገፋፋት በጨረፍታም ቢሆን ሊያሳይ የሚችለው ሌላኛው ሁነት ደግሞ ወ/ሮ አና ጎሜዝን አስመልክቶ ሊነሳ የሚችለው ነው፡፡ በረከት «የሁለት ምርጫዎች ወግ» በሚለው መጽሐፉ «የቅኝ-ገዥነት መንፈስ ያልለቀቃት» ብሎ የገለፃትን አና ጎሜዝ (የመለስ በስድብ የተሞላ የኢትዮጵያን ሄራልድ ጋዜጣ መጣጥፍ ሳይዘነጋ)፣ ከሁለት ወራት በፊት አዲስ አበባ

በመጣችበት ወቅት አባዱላ በጓዳዊ ስሜት እንዳስተናገዳት ራሷ ከመመስከሯም በዘለለ፣ እነርሱም በአዲስ ዘመን ጋዜጣቸው «እየተመካከርን ነው» የሚል የወዳጅነት መንፈስ የረበበበት የፎቶ ዘገባ ማቅረባቸውን እናስታውሳለን፡፡ ይህች ተራ የምትመስል ሁነት ለበረከት የምታስተላልፈው መልዕክት ቢኖር ‹እናንተ እንደሰይጣን የረገማችሁትን ሁሉ እየተከተልን አንረግምም» የምትል እኩዮች ነን አይነት ትከሻ መጋፋት ትመስለኛለች፡፡

በአናቱም አባዱላ አብዛኛው የኦህዴድ አመራርን በዙሪያው ማሰባሰብ ስለመቻሉ ይነገራል፡፡ ከዚህ ቀደም በአደባባይ እስከመዘላለፍ የተደራረሱትን አቶ ሙክታር ከድርንም ከጎኑ ማሰለፍ ችሏል፡፡ በአንድ ወቅት የግል ጠባቂው የነበረውና አሁን የኦህዴድ ማዕከላዊ ኮሚቴ አባል የሆነው አብይ አህመድ በእንዲህ አይነቱ ጊዜ ውለታ ለመመለስ የሚያደርገው ተጋድሎ የማይናቅ ጠቀሜታ አስገኝቶለታል፡፡ የሰሞኑ ሹም ሽርም የራሱ የሆነ አንድምታ አለው፡፡ ህጋዊ ባልሆነ መንገድ በማዕከላዊ ኮሚቴ ድምጽ ከስልጣኑ የተሻረው የክልሉ ፕሬዚዳንት አለማየሁ አቱምሳ (እርሱን ማንሳት የሚችለው ጠቅላላ ጉባኤው ብቻ መሆኑን ልብ ይሏል፡፡ በርግጥ ሰውየው አሁን አልፏልና በባህላዊ ልማዳችን መሰረት ነፍስ ይማር ብለን እናልፋለን) በ2002ቱ ምርጫ ማግስት አቶ መለስ ከካድሬዎቹ ይሁንታ ውጪ አባዱላን ለመተካት ያመጣው እንደነበር ይታወሳል፡፡ (በነገራችን ላይ በወራት እድሜ ውስጥ በመለስ የተሾሙ የክልል ፕሬዚዳንቶች ከኃላፊነታቸው ሲነሱ ከሽፈራው ሽጉጤ እና አያሌው ጎበዜ ቀጥሎ አለማየሁ አቱምሳ ሶስተኛው ሰው መሆኑ ነው) የድርጅቱ ሊቀ-መንበር እና ምክትል ሆነው የተመረጡት ሙክታር ከድርና አስቴር ማሞም የአባዱላን የበላይነት ለመቀበል ግለ- ሂሳቸውን ውጠዋል፡፡ ይህም ሆኖ የክልሉ አስተዳዳሪ ማን ይሆናል? የሚለው ጥያቄ ገና መልስ አላገኘም፡፡ ምናልባት (ከስራ አስፈፃሚዎችም መካከል መምረጥ እንደሚቻል ታሳቢ ተደርጎ) በሌሎች አካባቢዎች እንደታየው ከድርጅቱ ሊቀ-መናብርት (ሙክታርና አስቴር) አንዳቸውን መሾም ቢፈልጉ እንኳ ዕውን የሚሆንበት ዕድል የለም፡፡ ምክንያቱም እነርሱ የህዝብ ተወካዮች እንጂ የጨፌ ኦሮሚያ ም/ቤት አባል አይደሉምና፡፡ በእኔ ግምት እስከሚቀጥለው የምርጫ ዘመን ድረስ ቦታው አዲስ ሰው ሳይሰየምበት በምክትል ፕሬዚዳንቱ አብዱል አዚዝ ስር እንዳለ የሚቆይ ይመስለኛል፡፡

ከምርጫው በኋላስ? ….አፈ-ጉባኤው በኦህዴድ ውስጥ ለማስፈን እየሞከረ ካለው «አምልኮ አባዱላ» ተነስተን «ተገፈተርኩበት!» የሚለውን ያደረ ቁጭቱን ስንደምርበት ወንበሩን ራሱ ይይዘው ይሆናል ከሚል ጠርዝ ያደርሰናል፤ አሊያም ከሽርኮቹ ሙክታር ከድር እና ወርቅነህ ገበየው አንዳቸውን አሾሞበት በጨፌ ኦሮሚያም የሚካኤል ስሁልን መንፈስ ማንበሩ አይቀርም ብሎ ቅድመ ግምት ማስቀመጥ ይቻላል (ይህ መላምት የህወሓት-ብአዴን ጥንካሬ በዚሁ ከቀጠለ እና የእነርሱ ፍላጎት ደግሞ የተለየ ከሆነ ከህልም ሊዘል አለመቻሉን በማመን ላይ የተመሰረተ ነው)

ኦህዴድን ካነሳን የሌንጮ ለታን ኦዴግን መፃኢ እድልም መመልከት ግድ ይለናል፤ ምክንያቱም ኦዴግ አገር ውስጥ ገብቶ በሰላማዊ መንገድ መታገል ወስኖ ጨርሷልና፤ ሂደቱንም ለማመቻቸት ከግንባሩ መሪዎች አቦ ሌንጮ ለታ፣ ዶ/ር ሌንጮ ባቲ፣ ዶ/ር ዲማ ነጎዎ፣ ዶ/ር ታደሰ ኤባ እና ዶ/ር በየነ አሰቦ ጋር ከስምምነት ለመድረስ፣ ኢህአዴግ በውጪ ሀገር ከሚገኙት የጄኔራል ታደሰ ብሩ ልጆች በተጨማሪ፣ ፕ/ር እንድሪያስ እሸቴ፣ ፕ/ር ኤፍሬም ይስሃቅ፣ ፓስተር ዳንኤል፣ ሻለቃ ኃይሌ ገ/ስላሴ፣ ሻለቃ ደራርቱ ቱሉ፣ አባቢያ አባጆቢር፣ አቶ በቀለ ነዲ (የአዋሽ ባንክ የቦርድ ሰብሳቢ የነበሩ)፣ ወ/ሮ ሙሉ ሰለሞንን የመሳሰሉ አደራዳሪዎችን ማሳተፉ ይነገራል፡፡

ይህም ሆኖ ድርድሩ በስኬት ተቋጭቶ ኦዴግ ሀገር ቤት መግባት ቢችል እንኳ፣ ኦህዴዶች ‹አያሰጋንም› የሚል እምነት እንዳላቸው ሰምቻለሁ፡፡ ግና፣ ያለፉት ሁለት አስርታት ዘግናኝ ክስተቶች አሻራ ዛሬም በረዣዥሞቹ የባሌ ተራሮች በጉልህ ተቸክችኮ የመታየቱ እውነታ፣ በስርዓቱ ላኮረፈው የኦሮሚያ ህዝብ፣ ኦዴግን አማራጭ የሚያደርግበት «አኪር» ሸሽጎ ይዞ እንደሆነ ማን ያውቃል? ይህ እንግዲህ እነ ሌንጮ «ካዳሚ» ለመሆን አይመጡም በሚል ስሌት ከተቃኘ ነው፡፡ ይሁንና ከድርድሩ ጀርባ ያለውን እንቆቅልሽ ለመፍታት ጊዜ የሚጠይቅ ቢሆንም፣ ጉዳዩን ውስብስብ የሚያደርጉ ክስተቶችን ግን መጥቀስ ይቻላል፡፡ ይኸውም በአፈ-ጉባኤ አባዱላ ፊት አውራሪነት ስር ለመጠናከር እየሞከረ ያለው ኦህዴድ፣ ከሰዎቹ ሀገር ቤት መግባት ምን ያተርፋል? ምንስ ያጣል? ከሚለው ጋር ይያያዛል፡፡

መቼም የኦዴግን መምጣት፣ ኦቦ ሌንጮ «እንጮቴ» (ተወዳጅ ባሕላዊ ምግብ ነው) በአይኑ ላይ እየተመላለሰ እንደሆነ ከሰነዘረው ቀልድም ሆነ «ከሌሎች የኦሮሞ ህዝብ ዴሞክራሲያዊ ድርጅቶች ጋር በመተባበር ዘመናዊ ፌደራሊዝምን እመሰርታለሁ» ብሎ በደምሳሳው ከገለፀው ዓላማው ጋር አያይዞ ማለፍ አይቻልም፡፡ አሊያም ያኔ እርሱ ሸገርን ተሰናብቶ ሲወጣ ገና ያልፀደቀውን አንቀፅ 39ን «አስፈፅማለሁ» በሚል ቀቢፀ-ተስፋ ተገፍቶ ነው ማለትም አይቻልም፡፡ በግልባጩ አንዳንድ የፖለቲካ ተንታኞች ‹የኦዴግ መሪዎች በኦነግ ዘመን ለእስር የዳረጓቸውን በሺ የሚቆጠሩ የኦሮሚያ ተወላጆችን ለማስፈታት ሲሉ፣ በታማኝ ተቃዋሚነት ለመታገል ወስነው ነው የሚመጡት› የሚለውን መከራከሪያቸውን ለመቀበል የሚቸግረው ደግሞ፣ እስረኞቹን መፍታት ለሃያ አመታት ያህል በክልሉ ላይ ሰላማዊ ዜጎችን በማሰር የሚታወቀውን ኦህዴድን ሊያሳጣ የመቻሉ ነገር ነው፡፡ ያም ተባለ ያ፣ «ለሁሉም ጊዜ አለው» እንዲል ጠቢቡ
tplf-rotten-apple-245x300
ሰለሞን ሁሉም ቋጠሮ ጊዜ የሚፈታው ይሆናል፡፡ አሁን ላይ እርግጠኛ መሆን የሚቻለው በኦህዴድ ውስጥ አባዱላ ገመዳ ወሳኝ እየሆነ የመምጣቱ እውነታ ብቻ ነው፡፡

ህወሓት-ብአዴን

በዋናነት ሀገሪቷን እንደሚያሽከረክሯት የሚነገርላቸው ህወሓት እና ብአዴን፣ በመጪዎቹ ጊዜያት ‹ኢህአዴግ ለዳግም ክፍፍል ሊዳረግ ይችላል› በሚል ፍርሃት ድርና ማግ ሆነው እየሰሩ ስለመሆኑ እየሰማን ነው፡፡ በርግጥ ‹መለስ ህወሓትን አዳክሞ ነው ያለፈው› የሚል የትግርኛ ተናጋሪዎች ድምፅ መሰማት ከጀመረ ሰነባብቷል (በነገራችን ላይ ከ2000 ዓ.ም ወዲህ የህወሓትን የምስረታ በዓል የካቲት 11ን በብሔራዊ ደረጃ ማክበር መቅረቱን በይፋ ከማወጃቸውም በላይ፣ መለስ ራሱ ለመጨረሻ ጊዜ በመቀሌው የሰማዕታት አዳራሽ የተገኘው 35ኛው ዓመት በተከበረበት ወቅት ነበር፡፡ ይሁንና ከህልፈቱ በኋላ ድርጅቱ የደረሰበትን ድክመት ለመሸፋፈን በደመቀ መልኩ እያከበረው ይገኛል፤ ለዚህም ይመስለኛል በአምናውም ሆነ በዘንድሮው በዓል ላይ ጠቅላይ ሚንስትር ኃይለማሪያም ደሳለኝ መቀሌ የሞቀ ተገኝቶ ንግግር ከማድረግም አልፎ ከሱዳኑ ፕሬዚዳንት ኡመር ሀሰን አልበሽር ጋር በትግሉ ዘመን በተቀነቀኑ ዜማዎች ሲደንስ በቴሌቪዥን መስኮት ተመልክተን ሦስተኛው ሚሊንየም ገባ እንዴ? ብለን ግራ የተጋባነው፡፡ አልበሽርስ አንድ ቻርተር አውሮፕላን ለክልሉ በስጦታ ያበረከተው ዕውን በዓሉን አስመልክቶ ነው? ወይስ በምትኩ የተሰጠው ነገር ኖሮ? መቼም የህወሓት የምስረታ በዓል እንዲህ ሊያስፈነጥዘው እይችልም)

deberestion‹ህወሓት ተዳክሟል› የሚለውን ቅሬታ የሚያሰሙ የቅርብ ሰዎች፣ ድርጅቱ አቅምና ልምድ በሌላቸው መሪዎች ስር ማደሩን ይጠቅሳሉ፡፡ ተስፋ የጣሉበት ዶ/ር ደብረጽዮን ገ/ሚካኤልም ቢሆን ከአምባገነንነቱም በላይ ሀሳቡን አፍታቶ የማስረዳት ችሎታው ደካማ መሆን መፍትሄውን አርቆ ሰቅሎታል፡፡ እንደ ድርጅቱ የቅርብ ሰዎች አገላለፅ የ«ጠንካራ ተተኪ» አልቦነትን ለመረዳት፣ በቅርቡ ከኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ኃላፊነቱ በተነሳው አቶ ዘርዓይ አስገዶም ቦታ ላይ የዋልታ ስራ አስኪያጅ መመደቡ እና ራሱ ዘርዓይም በጓሮ በር የብሮድካስት ባለስልጣን ሆኖ መሾሙን (አዲስ ፊት አለመታየቱን) መመልከቱ በቂ ነው፡፡ በቅርቡ የዶክትሬት ዲግሪውን ያገኘው አርከበ እቁባይም ለአመራርነት ለቀረበለት ጥያቄ እያንገራገረ እንደሆነ ተሰምቷል፤ አቦይ ስብሃት ነጋም ኢ-መደበኛ በሆነ የጠረጴዛ ወግ ህወሓት «በግብር በላ» መሪዎች እጅ መውደቁን በቁጭት መናገራቸው ይጠቀሳል፡፡ ይሁንና በዚህ ቀውጢ ወቅት ሁለት ተቋማት ድርጅቱን ለጊዜውም ቢሆን ፖለቲካዊ ጉልበቱን እንዳይነጠቅ ታድገውታል፡፡ ደህንነቱ እና ሰራዊቱ፡፡

የሆነው ሆኖ ህወሓት ዛሬም ከብአዴን ጋር በማበር (በአባይ ፀሐዬ እና በበረከት ስምኦን የፊት መሪነት) የፖለቲካው አሽከርካሪነቱን እንዳስከበረ ይገኛል፡፡ ሁለቱ ሰዎች የስርዓቱን ርዕዮተ-ዓለምንም (በተለይም አብዮታዊ ዲሞክራሲን) ከሌሎች ጓዶቻቸው በበለጠ ማብራራት እንደሚችሉ ይነገራል፡፡ በጅጅጋ ከተማ የብሔር ብሔረሰቦች ቀን በተከበረበት ወቅትም ሆነ ከሳምንታት በፊት በመቀሌ ከተማ በተዘጋጀ መድረክ አባይ ፀሐዬ የርዕዮተ-አለሙ «ተንታኝ» ሆኖ የቀረበው ከዚህ አኳያ ነበር፡፡ በአናቱም አባይ እና በረከትን ጨምሮ ከኦህዴድ ኩማ ደመቅሳ፤ ከደኢህዴን ዶ/ር ካሱ ኢላላ የጠቅላይ ሚኒስትሩ የፖሊሲ ጥናትና ምርምር አማካሪ ሆነው መሾማቸው ይታወሳል፡፡ በዋናነት ለኢህአዴግ የስልጣኑ መሰረት (ከታጠቀው ኃይል እና ኢኮኖሚያዊ ጥንካሬው በተጨማሪ) ‹በልማታዊ መንግስት፣ በጥርነፋ፣ ሳር-ቅጠሉን በማደራጀት፣ የብሔር ጉዳይን በማጎን እና መሰል ጭብጦችን በማስጮኽ የሚያምታታበት ርዕዮተ-ዓለሙ እንደሆነ ይታወቃል፡፡ የእነ በረከት የተሰሚነት ምስጢርም ከዚሁ ጋር የተያያዘ ነው፡፡ በርግጥም የካቲት 14 ቀን 2006 ዓ.ም. የተሰበሰበው የሚኒስትሮች ምክር ቤት የፖሊሲ ጥናትና ምርምር ማዕከልን ለማቋቋም የሚያስችል ደንብ ማፅደቁን እና የአራቱም ድርጅት የአመራር አባላት የተወከሉበት ከመሆኑ አኳያ፣ ቦታው ከማማከር የዘለለ የስራ ድርሻ እንዳለው መገመት አያዳግትም (በነገራችን ላይ የመለስ ፖለቲካ ሰለባ የሆነው የብአዴኑ ተፈራ ዋልዋ ድምፁን አጥፍቶና ከውጥንቅጡ አርባ ክንድ እርቆ በእንጦጦ ተራራ እና በረዣዥም ህንፃዎች አናት በመፈናጠጥ ቴሌስኮፑን ግራና ቀኝ እያዟዟረ ከዋክብት ሲመለከት መዋልን አይነት ፀጥተኛ ህይወት፣ አንዳንድ የቀድሞ ጓዶቹም ለተረፈቻቸው እድሜ የሚመኙት ይመስለኛል)

ለውጥ ይኖር ይሆን?

የስርዓቱ ልሂቃን ብሔሮቻቸውን ማዕከል ባደረገ መልኩም ይሁን፣ በሥልጣን ከፍታ ከሚያገኙት ግላዊ ጥቅማ-ጥቅም በመነሳት፣ ከላይ ለመተንተን እንደሞከርኩት ባለ የመከፋፈል መሰል ሂደት ውስጥ እንኳን ቢያልፉ በቀጣይ ጊዜያት ‹የፖለቲካ ማሻሻያ ያደርጋሉ› ብሎ ለማመን ነገሮች በእጅጉ አስቸጋሪ ናቸው፡፡ ለዚህም ሶስት ነጥቦችን እናንሳ፡- የመጀመሪያው የሀገሪቱ የደህንነት መዋቅር አደረጃጀት ባህሪ ነው፡፡ እንደሚታወቀው በእነ ጌታቸው አሰፋ የሚመራው የደህንነት ተቋም በሚታዩና በማይታዩ ድርጊቶች ለህወሓት የተገዛ ነው፡፡
ከዚህች ሀገር ጀርባ ለተፈፀሙም ሆነ ገና ለሚፈፀሙ ድርጅታዊ እና ግለሰባዊ (ባለሥልጣናዊ) ወንጀሎች አስፈፃሚና በደል አንፂ ነው፡፡

ሐረር በእሳት አደጋ፣ በጥይት ሩምታ፣ በሕዝባዊ ተቃውሞና በቆመጥ ድብደባ ስትታመስ ዋለች

$
0
0

(ዘ-ሐበሻ) በሐረር ትናንት ምሽት ከግምት ከሶስት ሰዓት ተኩል ጀምሮ ልዩ ስሙ መብራት ሃይል ተበሎ በሚታወቀው የገበያ ቦታ በተነሳ እሳት አደጋ የበርካታ ነጋዴዎች ንብረት ከወደመ በኋላ “የእሳት አደጋውን የክልሉ መንግስት ሆን ብሎ ያቀነባበረው ነው” በሚል የአካባቢው ነዋሪ በዛሬው ዕለት ተቃውሞን ለመግለጽ አደባባይ ወጥቶ እሳቱን ለማጥፋት ውሃ ያልነበረው የክልሉ የእሳት አደጋ ማጥፊያ የተቃውሞ ሰልፈኛውን ለመበተን ውሃና አስለቃሽ ጭስ ሲጠቀም ዋለ። የክልሉ ፖሊስም በጥይት ሩምታ በማውረድ፣ በቆመጥ በመደብደብ ሰልፈኛውን ሲበትን መዋሉን ለዘ-ሐበሻ ከስፍራው የደረሱ ዜናዎች አመልክተዋል።
harar city fire

Harar City
የዘ-ሐበሻ ተባባሪ ዘጋቢዎች ከሐረር በትናንቱ የእሳት አደጋ ቃጠሎ ንብረታቸው ከወደመባቸው መካከል የተወሰኑትን በማነጋጋር ባጠናቀሩት መረጃ “የክልሉ መንግስት ነጋዴዎቹ ይሰሩበት የነበረውን ቦታ ይፈልገው ነበር። በተደጋጋሚም እንዲነሱ ጠይቋል። ነጋዴዎቹ ከዚህ ቀደም ከ3 ዓመታት በፊት ሸዋበር አካባቢ በተመሳሳይ ሴራ ንብረታቸው የተቃጠለባቸው መሆኑን እና በትናንቱ አደጋ ንብረታቸው ሙሉ በሙሉ በመውደሙ ለተቃውሞ አደባባይ እንዳስወጣቸው መረዳት ችለናል።

በመብራት ሃይል የገበያ ቦታ የተነሳው እሳትን ለማጥፋት የተደረገው ርብርቦሽ በጣም ደካማ እንደነበር የሚገልጹት እነዚሁ ነጋዴዎች ከድሬደዋ እና ከጅጅጋ የእሳት አደጋ ማጥፊያ ብርጌድ እስኪመጣ ድረስ ብዙ ንብረት ወድሟል። እሳቱ ሳይስፋፋ ነጋዴዎቹም የተወሰነ ንብረት እንኳ ከእሳቱ እንዲያተርፉት አለመደረጉን የገለጹት እነዚሁ ባለንብረቶች መንግስት ወዲያውኑ የተቃጠለውን አካባቢ በግሬደር ማረሱ አስገራሚ ሆኖባቸው ነጋዴዎቹ ዛሬ አደባባይ ወጥተው ተቃውሟቸውን ሲያሰሙ ነበር።

በብሶት የተወጠረው የሃረር ሕዝብ ባስነሳው ተቃውሞ የክልሉ ፖሊስ በአስለቃሽ ጭስ፣ በቆመጥ ድብደባ፣ በውሃ፣ በጥይት ሲበትን የዋለ መሆኑን የገለጹት የዘ-ሐበሻ ዘጋቢዎች በርካታ ሰዎች መታፈሳቸውንም ገልጸዋል።

በዚህ የተቃውሞ እንስቃሴ ላይ የሞተ ሰው እንዳለ ለማረጋገጥ ያደረግነው ሙከራ ባይሳካም በርካታ ሰዎች መቁሰላቸው ግን ተሰምቷል።

ተጨማሪ መረጃዎች እንደደረሱን እንመለሳለን።

ዉርደት በጩኸት ብዛት ክብር አይሆንም

$
0
0

ባንድ ወቅት የቀዲሞ የኢትዮጵያ አየር ወለዶች ግዳጅ ተሰቶዋቸው በተሰማሩበት ዉጊያ ከባድ ድካም ዉስጥ በመግባታቸው የመፍረክረክ ሁነታ ይታያል በዚህን ጊዜ የብርጌዱ አዛዥ ኮሎነል ግሩም አበበ የምን መፍረክረክ ነዉ፣ አየር ወለድ ግንባሩን እንጂ ጀርባዉን አይመታም፣ በሉ ተከተሉኝ ብሎ ሳንጃዉን ወድሮ የጅቦምቡን ቅርቃር ነቅሎ ወደፊት ተንደረደረ። ሰራዊቱም ተከተለዉ ለሰዓታት ከምሽግ ምሽግ አይዘለለ ስዋጋ እና ሲያዋጋ ጦሩም በጠላት ላይ አያየለ መጣ፤ ከተወሰኑ አርሚጃወች በሖላ ኮሎኔል ግሩም ከፍጥነቱ አየቀነሰ በጉልበቱ በርከክ አለ፣ ወዲያዉም በሙሉ ሰዉነቱ መሬት ላይ አረፍ አለ። ከወዲወድያ እየተሯሯጡ ይዋጉ የነበሩ ኮማንዶች እንደገና ኮሎኔሉ አጠገብ መሰባሰብ ሲጀምሩ፣ እኔ ደሕና ነኝ ዉጊያዉን ቀጥሉ ብሎ ጋደም አለ። የተወሰኑ ወታደሮች ደግፈዉ አንዲት ዛፍ አስደግፈዉት በእልህ ወደ ዉጊያዉ ሮጡ። የመሰላቸዉ ላለፉት አርባ ስምንት ሰዓታት ምግብ ስላልቀመሰ ደክሞት ይሆናል ብለዉ ነበር። ከሰአታት አስቸጋሪ ትንቅንቅ በሖዋላ ጠላትን ደምስሰዉ ፩፮ኛ ሰንጥቅ መከናይዝድን ከከበባዉ በማዳን የተሰጣቸዉን ቦታ ከተቆጣጠሩ በሆዋላ በድል ወደ ኮሎኔል ግሩም በመሮጥ ድሉን ለማብሰር ስመጡ፣ ኮሎኔል ግሩም አበበ የ፭ኛ አየር ወለድ ብርጌድ ኣዛዥ ቅድም አንደተራ ወታደር በየሚሽጉ አይዘለለ ስዋጋ ተመቶ ኖሮአል ግራ ጎኑ በደም ርሶ የጦርነቱን መጠረሻ ሳያይ፣ ልጆቼን፣ በተሰቤን፣ ሳይል ለአገሩ ሲል አንዲት ሂይወቱን በመስጠት ለዘላለሙ አንቀላፍቶ አገኙት ።(የጦር ሜዳ ዉሎን ያንብቡ)

ኢትዮጵያ ብዙ ግሩሞች ነበሩዋት። ከነሱ ኣልፎ ለሌላዉ የምተርፍ ብዙ እዉቀት ብዙ ነገር እያላቸዉ ብቸኛ ህይወታቸዉን ለአገራቸዉ ክብር የሰጡ፤ ለነብሳቸዉ ሳይሳሱ የማይቻል የመሰለ መስዋእትነት የከፈሉ፣ ከዉርደት ይልቅ በክብር መሞትን የመረጡ። ኢትዮጵያ በጣም ብዙ ግሩሞች ነበሩዋት ከምንዳ ከገንዘብ ከትራፊና ከፍሪፋሪ ይልቅ ስለኣገራቸዉ መራብን የመረጡ። ኢትዮጵያ ብዙ ግሩሞች ነበሩዋት በሚሊዮን የሚቆጠር ገንዘብ የሚያስገኝ አውቀታቸዉን ለሚስኪኑ ህዝባቸዉ ሲሉ ንቀዉ በድህነት ኖረዉ በድህነት የሞቱ። ኢትዮጵያ ዛሬም ብዙ ግሩሞች አሉዋት ገድላቸዉ አንድ ቀን የሚወራላቸዉ፣ እነ አስኪንድሮች፣ እነአንዱአለሞች፣ እነርዮቶች፣ እነበቀለወች፣ እነኦልባናወች፣ እነናትናኤሎች፣ እነዉብሸቶች፣እነ እነ እነ እነ እነ ብዙ ብዙዎች።

ኢትዮጵያ ለሎችም አሉዋት ሆድ አምላካቸዉ፣ ዉርደት ክብራቸዉ፣ ክሂደት ዝናቸዉ፣ ዉሸት እዉቀታቸዉ፣ ባርነት ስብዕናቸዉ፣ እነብርሃኑ ዳምጤወች (ኣባመላ የሚለዉ ስም ሰልማይመጥነዉ ነዉ)።

aba melaዉርደት በጩኸት ብዛት ክብር ላይሆን ኢትዮጵያ ብዙ ከርሳሞች ሞልተዋታል የተደገሰ ቦታ የማይጠፉ በልተዉ የማይሄዱ አንደዉሻ ካልጮሁ ።ከጢቂት ወራቶች በፍት በሳኡዲ አረቢያ ኢትዮጵያዊያኖች ሲታረዱ ብዙሆች ጮኸዉ ነበር አብዛኛዉ ኢትዮጵያዊ ከጢቂት ከርስ አደሮች ጋር ሆነዉ። ዛሬ ከርስ አደሮቹ ከርሳቸዉን ወደ ሚሞሉበት ሲመልሱ አሁንም ኢንጮሃለን ከዱን ብለን። የሳኡዲ ጥቃት ሲያበሳጨን ጮኸን ፣ሆድ አደሮች ሲከዱንም ጮኸን አንችልም፣ ነብሰገዳዮች አገራችንን ሲበታትኑ ጮኸን ለዉጥ አላመጣንም፣ ቅርሳችን መለያችን ለባዳዎች ሲሳይ ሲሆን ጮኸን ጠብ ያለልን ነገር የለም። በጩኸት ብዛት ለነሆድ አደሮች ክብር እንደማይመጣ ሁሉ ለተቀረነዉም የነሱ አይነት ጩኸት ነጻነት አይሰጠንም። ነጻ የሚያወጣን እንደነ ግሩም አበበ ደም መክፈል ስንችል ብቻ ነዉ።ነጻ የሚንወጣዉ በአመንንበት ነገር ላይ ጸንተን መቆም ስንችል ብቻ ነዉ። የታላቁን ኢትዮጵያዊ የዓባመላን ስም ቅጥሉ አንዳደረገዉ አሳማ ወደነፈሰበት ብንዘም ውርደትን አንደ አካላችን ከማየት ያለፈ ነገር አይኖረንም፣ እንደ ኮሎኔል ግሩም ስንጸና ቢያንስ ሞታችን እንኩዋን በኩራት ዘንተ አለም ይነገራል። ሳኡዲወች አዋረዱን ብለን ስንጮህ የነበርነዉ በስተት ነበር ምክኒያቱም አራሳችንን ያዋረድነዉ አራሳችን መሆናችንን ስላልተረዳን። ብዙሺ ግሩሞች ጠዉልገዉ ያቆዩአትን አገራችይንን ለእነ አባአተላ ፣ለነ አባባንዳ፣ ለነ አባሆድ አምላክ፣አሳልፈን ሰተን ስደትን አንደመፍትሔ ቆጠርን በተሰደድንበትም ቢሆን ከነሱ መለየትን ባለመድፈር እራሳችንን አዋርደን ተዋረድን ኢንጂ በምንም መንገድ ሰኡዲወች አላዋረዱንም።

በምንም መንገድ አረቦች አላዋረዱንም ስብእናችንን አሳሞች ሲረጋግጡት መከላከል የተዉን፣ ከመሰሪዎች ጋር የተቆራኘን ጢቂቶች የተሻለ አማራጭ እያላቸዉ በሞታቸዉ ያስረከቡንን ነጻነት ዋጋ ያቃለልን እራሳችን እንጂ። በምንም መንገድ እራሳችንን ያዋረደን እኛዉ ነን፣ የእምቢ ጽናታችንን ከዉስጣችን አዉልቀን የጣልን፣ ከሃሰተኞች ጋር ቤተክርስቲያን የምናጣብብ፣ከአረመኔዎች ጋር መስግድ የሞላን ለእዉነት ካልቆሙ ለሃሰት ከምጸልዩ ጋር የተባበርን።አባቶቻችን ደም ከፍለዉ ያቆዩትን ነጻነት በፍርፋሪ ከሸጡ የሉኝንታ ካልፈጠረባቸዉ ከሃዲዎች ጋር እስከቆምን ድረስ እኛም ነጻነታችንን ለዘላለሙ እናጣዉ እንድሁ አንጂ መልሰን አናገኘዉም። መለየት የሚባልን ድፍረት የግድ መልመድ ካልተቻለ ዛሬም ነገም ብዙ ለሆዳችዉ ያደሩ ስያስጮሁን መኖራችን የማይቀር ነዉ። ጣይቱ በበቀለችበት ምድር ሊጁዋን እንዝርት ከማስያዝ ፋንታ ለዚሙት የምታሰማራን፣ ስብዕና በጎደላቸዉ አረቦች መጫወቻ ሆና አስክሬኑዋ የመጣን የጎሮቤት ልጃገረድ ቀብራ የራሱዋን የ፩፭ ዓመት ልጅ ባወጣዉ ያዉጣሽ ብላ መልሳ ወደዛዉ የምትልክን እናት፣የኮሎኔል ግሩም አይነት በሞሉባት ኢትዮጵያ ፣ ዛሬ እኔ ሞቼ ልጆቹን ከዉርደት ማዳን አለብኝ ከማለት ፋንታ እርሱም ፈርቶ ለመብታቸዉ የሚቆሙትን ሊጆቹን ለስደት ልኮ ባህር በላቸዉን ዜና ከሚጠብቅ አባት፣ መቀበሪያዉን ኢንኳን ለማትሞላ መሬት ማንነቱን የሸጠን ሰደተኛ ማህበረሰቡ በቃቹ ካላለ ፣ ለሆድ ማደር አገርን ማዋረድ ፣ ሃፍረት መሆኑ ቀርቶ ጥበብ በሆነበት ዘመን በሆድ አደሮች ጩኸት መደንቆራችን መልሰንም መጮሃችን ይቀጥል ኢንድሁ አንጂ ክብርን አያመጣም።ዉርደታችን የሚያበቃዉ የህዝብና የአገር ጠላቶች የሆኑትን የወያኔ ቅጥረኞች በቃቹ ብለን ፍትለፍት ለመጋፈጥ ስንቆርጥ ብቻ ነዉ።

Police-Addisዉርደታችን የምያበቃዉ ትላንት እነሱ ተቀጥረዉለት የነበረዉን ሻቢያን ኢንዳላገለገሉት ሁሉ ዛሬ ከእናንተ ጋር ተዋረደን ከምንኖር ሞት ያሉትን በምንም መስፈርት የሻብያ አሽከር ብላቹ ብትጮሁ አንሰማቹሁም የማለት ብቃት ስናገኝ ነዉ።

ዉርደታችን የምያበቃዉ ገንዘባችንን በማዉጣት ለነጻነት የምደረግን ትግል ለማገዝ ስንቆርጥ፣ አስፈላጊም ከሆነ ለዘላለም ተዋርዶ ከመኖር እንደ ግሩም በክብርም ብሆን ለመሞት መቁረጥ ስንችል ነዉ።

ዉርደታችን የሚያበቃዉ በየእስር ቤቱ እየማቀቁ ያሉትን ወገኖቻችንን ልቀቁ ካልሆነም እናንተ ሌቦችን ከስር ቤት ኢያስመለጣቹ ለስልጣን ኢንደበቃቹ እኛም የወገኖቻችንን በዸል ለመበቀል ቆርጠናል ስንል ነዉ።

ዉርደታችን የሚያበቃዉ ከ፴ ሺ ብር በላይ ደሞዝ ፣ስም ፣ ዝና፣ ክብር፣ አለምን መዞር በጁ እያለ የወገኑን ብሶት ለአለም በማሳየት ወሂኒ መጣልን እንደመረጠዉ ሀይለመድህን አበራ እምቢ ስንል ብቻ ነዉ።መቀራረብን በመሻት፣ መቻቻልን ለመፍጠር የሚደረግ ነገር ሁሉ ለቅጥረኞች ለሆድ አደሮች ካልገባቸዉ ከነሱ መለየት አማራጭም አቆዋራጭም መሆኑ ግድ ነዉ።

ያለን አማራጭ ሁለት ብቻ ነዉ፣
አንድም እንደ ኮሎኔል ግሩም አበበ ወደፊት ሄዶ ግንባርን ሰጥቶ በክብር ማለፍ ሁለትም ከነዉርደት ፵ የማትሞላዋን ዕድሜ መኖር። አንድም እንደ ሀይለመድህን አበራ ሃምሳ ዓመትም ቢሆን ወይኒ መጣል ሁለትም በገዛ አገሩ የመጨረሻ ደረጃ ዜግነት መቀበል። አንድም እንደባህር ዳር ህዝብ መቆጣት ሁለትም በባዶ እግሩ የሚሄድ ለሃጫም አየተባሉ መኖር። አንድም የዓዱዋን ጀግኖች ፈለግ መከተል ሁለትም የደደቢትን ሹምባሾች ካልሲ ማጠብ። አንድም ሰዉ ሆኖ መራብ ሁለትም እንደ አባመላ ተብየዉ ትፋትን ልሶ መጥገብ።
ያለዉን ምርጫ መለየት ካልተቻለ ዉርደትን ከክብር የቆጠሩ አሳሞች ስጮሁ በአሳሞቹ የበገኑም አትጩሁ ኢያሉ ስጮሁ ዉርደቱም ጩኸቱም ይቀጥላል ኢስከወዲያኛዉ።

አዩም አያኔ ዘ ኢትዮጵያ

pompidoayane@ymail.com

የሻምበል ፍቅረሥላሴ ወግደረስ አሳሳች መረጃዎችና የተምታታ አስተያየት

$
0
0

በመሠረቱ ሻምበል ፍቅረሥላሴ ወግደረስ ስለ አብዮቱ “ እኛና አብዮቱ “ የሚል መጸሐፍ ጻፉ የሚል
ዜና ስሰማ ፣ መጸሐፋቸው እንደ ሌ/ኮ መንግሥቱ ኃይለማርያም መጸሐፍ በቅጥፈት የተሞላ
አይሆንም ብዬ ተስፋ አድርጌ ነበር ፡፡ ግን ሳይሆን ቀረ ፡፡ በነገራችን ላይ የሻምበሉን መጸሐፍ ገና
አላገኘሁትም ፣ ነገር ግን አንድ ወዳጄ ከምዕራፍ 13–16 ያሉትን ገጾች ፎቶ ኮፒ አድርጎ ስለሠጠኝ
አየተገረምኩኝ አነበብኳቸው ፡፡ ሻምበሉን ምን ነካቸው ብዬም እራሴን ጠየኩኝ ፡፡ ደራሲው
በትምህርታቸው እንዳልገፉ ይገባኛል ፡፡ ሆኖም ግን በትምህርት ያለመግፋት ትንታኔ ላይ ችግር
ይፈጥር እንደሆን እንጂ ፤ “ በእጅ የገባን መረጃ ” አሳስቶ ማቅረብ ከምን ሊመነጭ እንደሚችል
ፈጽሞ ሊገባኝ አይችልም ፡፡ ፍቅረሥላሴ መረጃው በእጃቸው ከሌላቸው አርፈው መቀመጥ አለባቸው
እንጂ ባልሆነ ማስረጃ አንባቢን ማሳሳት የለባቸውም ፡፡ መረጃው በእርሳቸው በኩል መቅረቡ ደግሞ
የበለጠ አደገኛ የሚያደርገው ፣ ግለ-ሰቡ በደርግ ውስጥ በከፍተኛ ሥልጣን ላይ የነበሩ ሰለሆኑ
መረጃው አላቸው ተብሎ ስለሚገመት ነው ፡፡ ዕውቀት መቸም በሁለት መንግድ እንደሚገኝ
ይታወቃል ፡፡ አንደኛው መንገድ ቀጥተኛ የሚባለው ሲሆን ሌላኛው ደግሞ ቀጥተኛ ያልሆነው መንገድ
ነው ፡፡ ቀጥተኛ የምንለው ፣ በራሳችን ተመክሮ የምናገኘው ዕውቀት ሲሆን ፣ ቀጥተኛ ያልሆነው
ደግሞ ከሌሎች ሰዎች ተመክሮ የሚገኝ ነው ፡፡ እኝህ ደራሲ ግን ከሁለቱም የታደሉ አይመስለኝም ፡፡ የጻፉት መጸሐፍ በራሳቸው ዘመን ያውም ቁልፍ ተዋናኝ ሆነው በተሳተፉበት ወቅት ስለተከናወነ
ጉዳይ ከመሆኑም በላይ ፣ ስለወቅቱም የሚያወሱ መጸሐፍቶች በብዛት ተጽፈው ይገኛሉ ፡፡ አንዳንድ
ጉዳዮች ሊረሱ ስለሚችሉ ደራሲው መረጃዎችን ከነዚህ መጸሐፍቶችና ከምርመራ መዝገቦች ላይ
ማግኘት ይችሉ ነበር ፡፡ እርሳቸው ግን ይኸንን ሁሉ መቸገር የፈለጉ አልመሰለኝም ፡፡ እስቲ ትዝብቴን
እርሳቸው ከፍ ብየ በጠቀስኳቸው ምዕራፎች ውስጥ ካቀረቧቸው አስተያቶች አንዳንዶቹን እየመዘዝኩ
በመኢሶን ድርጅት ዙሪያ ባቀረቡት ነጥቦች ላይ ብቻ በማተኮር አስተያየቶቼን ለማቅረብ ይፈቀድልኝ ፡፡
I. የመረጃ ስህተቶችን በተመለከተ
ሀ – የሕዝብ ድርጅት አባላትን በተመለከተ
በሻምበል ፍቅረሥላሴ ወግደረስ መጸሀፍ የቀረበልን የተሳሳተና ያልተሟላ መረጃ (
ገጽ 230 )
1 . አቶ የወንድወሰን ኃይሉ
2 . አቶ መሥፍን ካሱ
3 . ዶ/ር ሰናይ ሌኬ
4 . ዶ/ር ነገደ ጎበዜ
5 . አቶ ኃይሌ ፊዳ
6 . ዶ/ር ፍቅሬ መርዕድ
7 . አቶ አሰፋ መድሀኔ
8 . አቶ እሸቱ ጮሌ (ዶ/ር መባል አለበት)
9 . ዶ/ር መለሰ አያሌው
10 . አቶ ተስፋዬ ሸዋዬ
11 . አቶ ባሮ ቱምሳ
12 . ዶ/ር በዛብህ ማሩ
13 . አቶ ዮሐንስ አድማሱ ናቸው ፡፡ ( አቶ ዮናስ አድማሱ ለማለት ፈልገው
መሰለኝ ) የሚገርመው ነገር ሌ/ኮሎኔል መንግሥቱ ኃይለማርያምም “ትግላችን” ብለው ባሳተሙት መጸሐፋቸው ላይ ቁጥሩን ወደ 11 ዝቅ አድርገውታል ፡፡ ሰዎቹ
ወይ ጃጅተዋል ፣ አለበለዚያም የማስረጃ ጥቅሙ ስለማይገባቸው ፣ አቀራረቡ ላይ
ደንታቢስ ናቸው ማለት ነው ፡፡ ስለዚህ አንባቢ የነርሱን ሥራ በሚያነብበት ወቅት
በጥንቃቄ ከሌሎች ማስረጃዎች ጋር እያመሳከረ መሆን ይኖርበታል ፡፡
በአቶ አንዳርጋቸው አሰግድ “በአጭር የተቀጨ ረጅም ጉዞ” የቀረበልን ትክክለኛና
የተሟላ መረጃ (ገጽ 296 )1 . አቶ ኃይሌ ፊዳ
2 . ዶ/ር ፍቅሬ መርዕድ
3 . ዶ/ር ከድር መሐመድ ( በኋላ ላይ ወደ ኢሉ አባቦራ የሕዝብ ድርጅት ጽ/ቤት
የተዛወረ )
4 . አቶ መስፍን ካሱ
5 . ዶ/ር ነገደ ጎበዜ
6 . አቶ ባሮ ቱምሳ
7 . አቶ ዮናስ አድማሱ
8 . ዶ/ር ሠናይ ልኬ
9 . አቶ ሸዋንዳኝ በለጠ
10 . ዶ/ር እሸቱ ጮሌ
11 . ዶ/ር መለስ አያሌው
12 . ዶ/ር አሰፋ መድኀኔ
13 . አቶ ተስፋዬ ሸዋየ
14 . ዶ/ር በዛብህ ማሩና
15 . አቶ የወንድወሰን ኃይሉ – ከነዚህ ውስጥ ዶ/ር እሸቱ ጮሌና አቶ ዮናስ
አድማሱ ከጽሕፈት ቤቱ እንደተሰናበቱ ፣ በምትካቸው ዶ/ር ንግሥት አዳነና ዶ/ር ዓለሙ
አበበ ተጨምረዋል ፡፡ ከነዚህም ሌላ በኋላ ላይ የአፋር ነፃነት ንቅናቄ መሪ አባል የነበረው
አቶ ዩሱፍ ያሲን የጽ/ቤቱ አባል ሆኗል ፡፡ ለ – ከአዲስ አበባ ህቡዕ የገቡትን የመኢሶን አባሎችን በተመለከተ
በሻምበል ፍቅረሥላሴ ወግደረስ የቀረበልን ያልተሟላና የተሳሳተ መረጃ ( ገጽ 342-3 )
1ኛ ቡድን ፡- በጎጃም በር በሱልልታ በኩል ለመውጣት የሞከረ ፤
 ኃይሌ ፊዳ የቡድኑ መሪ (በነገራችን ላይ ህቡዕ ስንገባ ቡድን መሪ የሚባል
አልነበረንም ፡፡ ደራሲው ከየት እንዳመጡት አላውቅም ፣ ምናልባት በወታደር
ዓለም ውስጥ ያለ ቡድን መሪ መንቀሳቀስ አይቻልም መሰለኝ ?)
 ዳንኤል ታደሠ
 ዶ/ር ከበደ መሸሻ ( የዶ/ር ከበደ አባት ሥም ፣ መሸሻ ሳይሆን መንገሻ ነው )
 ደረጀ ዓለማየሁና ጥቂት የመኢሶን ካድሬዎች ፡፡ 2ኛ ቡድን ፡- በወለጋ በኩል ሊወጣ የሞከረ ፤
 ተፈራ ገ/ፃዲቅ የቡድኑ መሪ (ግለሰቡ ስማቸው ተፈራ ገ/ፃዲቅ ሳይሆን ፣ዶ/ር
ተረፈ ወልደፃድቅ ነው፡፡
 ዳነቢ ዲሳሳ የተፈራ ገ/ጻዲቅ ሚስት ( ደንቢ ዲሳሳ እዚህ ቡድን ውስጥ
አልነበረም )
 አማረ ተግባሩ
 መርዕድ ከበደ
 ኃይሉ ገርባባና ሌሎች የመኢሶን አባላትና ካድሬዎች ፡፡ ( ኃይሉ ገርባባ በዚህ
ቡድን ውስጥ አልነበረም ፡፡ እርሱ ከወለጋ ካድሬዎች ጋር ነው የወጣው )
3ኛ ቡድን ፡- በጂማ መስመር ለመውጣት የሞከረ ፤
 ኃይለሥላሴ ወ/ ገሪማ የቡድኑ መሪ
 በለጠ ወትሮና ሌሎች የመኢሶን አባላት ፡፡ 4ኛ ቡድን ፡- በሲዳሞ በኩል ለመውጣት የሞከረና በከፊልም ቢሆን የመትረፍ ዕድል
የገጠመው
 መስፍን ካሱ የቡድኑ መሪ
 ዶ/ር ንግሥት አዳነ ( ከዚህ ቡድን ጋር አልነበሩም ) ደስታ ታደሰ (ከዚህ ቡድን ጋር አልነበሩም )
 ዳዊት አሰፋ
 አበራ የማነአብ
 አንዳርጋቸው አሰግድ ናቸው ፡፡ በዚህ ጽሑፍ አቅራቢ ተሟልቶ የቀረበ
ወደ ጫንጮ የተጓዙ ጓዶች
 አቶ ኃይሌ ፊዳ
 ዶ/ር ከበደ መንገሻ
 አቶ ዳንኤል ታደሠ
 አቶ አያሌው ወልደ መድህን
 አቶ አበበ ኃይሌ
 አቶ የራስወርቅ አድማሴ
 አቶ ደረጀ ዓለማየሁ
 አቶ ዳንኤል (የትግል ስም ፣ ሾፌር ሆኖ ያገለገለ)
 ደንቢ ዲሳሳና ምትኩ ተርፋሳ ባካባቢው የሕዝብ ድርጅት ጽ/ቤት ባልደረባ
ስለነበሩ ከዚህ ቡድን ጋር አብረው ነበሩ ፡፡ ወደ አምቦ የተጓዙ ጓዶች
 ዶ/ር ተረፈ ወልደፃድቅ
 ወ/ሮ አጥናፍዓለም ይማም ( የዶ/ር ተረፈ ባለቤት )
 አቶ ከበደ ደሪባ
 አቶ እዮብ ታደሠ
 አቶ መርዕድ ከበደ
 አቶ አማረ ተግባሩ
ወደ ከንባታና ሀዲያ የተጓዙ ጓዶች
 አቶ ደስታ ታደሰ
 ዶ/ር ንግሥት አዳነ
 አቶ ኃይለሥላሴ ወልደገሪማና
 አቶ ኤፍሬም ዳኜ ሲሆኑ ፤ አቶ በለጠ ሙቱሮ ከአዲስ አበባ የሔዱ ሳይሆን ፣
እዛው የአውራጃው የሕዝብ ድርጅት ጉዳይ ጽ/ቤት ሠራተኛ የነበሩ ናቸው ፡፡ ወደ ሲዳሞ የተጓዙ ጓዶች
 አቶ አበራ የማነአብ
 አቶ አንዳርጋቸው አሰግድ
 አቶ መስፍን ካሱ
 አቶ ግርማ ሥዩም
 አቶ ዳዊት አሰፋ
አቶ ጋሻው ታደሠ ናቸው ፡፡ የሚገርመው ነገር ሌ/ኮ መንግሥቱ ኃይለማርያምም ሆኑ ሻም / ፍቅረሥላሴም፣
መኢሶኖች የተገደሉት በገበሬዎች እንጂ በኛ አይደለም ብለው ሽምጥጥ አድርገው ይዋሻሉ ፡፡ ዕውነቱ ግን ፣
የኢትዮጵያ ገበሬ እኛን ስለደበቀን ብቻ አብሮን ከመታሰርም አልፎ በድብደባ ተሰቃይቷልም ፡፡ አብዳላ ሶኔሳ
የኢትዮጵያ ገበሬዎች ማኀበር ፕሬዘዳንት ሆኖ በአብዮት አደባባይ ገበሬውን ወክሎ ንግግር ባደረገበት ወቅት
በንንግግሩ ላይ ደርግን ስለእኛ ድንገተኛ መሰወር የጠየቀው ጥያቄ ፤ “ እነዚያ እንደሱካር ይጣፍጡን የነበሩት
ልጆቻችን ወዴት ገቡ “ ብሎ ነበር ፡፡ ከንግግሩ ቆርጣችሁ ካላወጣችሁት በማስታወቂያ ሚኒስቴር ቤተ- መጸሐፍት ይገኛል ፡፡ በከንባታና ሀዲያ የተሸሸጉት ጓዶችም የተያዙት እርሶ እንደሚሉት በገበሬዎች ሳይሆን ፣መንገድ መሪዎቹ በከተማው የሠዐት እላፊ ለውጥ መደረጉን ባለማወቃቸው የተነሣ ፣ በወቅቱ ከተማውን
በሚጠብቁ የከተማው ፖሊሶችና በቀበሌ ጠባቂዎች ነው ሊያዙ የቻሉት ፡፡ ከዚያም ገበሬዎቹም ጓዶቹም
አብረው ተይዘው አዲስ አበባ ከመጡ በኋላ ነው ፣ ሁለቱን ማለትም ዶ/ር ንግሥት አዳነንና አቶ ደስታ
ታደሠን ከእስር ቤት ( ከከርቸሌና ከ4ኛ ክፍለ ጦር ) አውጥታችሁ ከነ ጓድ ኃይሌ ፊዳ ጋር አብራችሁ
የገደላችኋቸው ፡፡ ሀቁ ይኸው ነው ፣ የናንተም የምርመራ ሠነድ ቢፈተሸ ይኼንኑ ሀቅ ነው የሚመሰክረው ፡፡ ለምን የእናንተን ወንጀል በገበሬው ላይ እንደምታሳብቡ አይገባኝም ፡፡ እረስተውት ነው እንጂ ፣ በወቅቱ
ያስተላለፋችሁት ትዕዛዝ እኮ በተገኙበት ይገደሉ የሚል እንጂ እጃቸውን በሠላም ከሠጡ ያዟቸው የሚል
አልነበረም ፡፡ አንድ ቀን ይኸም የሕትመት ብርሃን ማየቱ አይቀርም ፡፡ እናንተ ያኔ የሚታያችሁ የነበረው
የተማረውን ክፍል አስወግዳችሁ ሥልጣን አለተቀናቃኝ መጨበጣችሁ ነው እንጂ ፣ አገሪቷንና አብዮቱን
ይዛችሁ ገደል መግባታችሁ አልታያችሁም ፡፡ አሁንም ለሠራችሁት ወንጀል ንሰሀ የገባችሁ አይመስለኝም ፡፡ ይኼ እንግዲህ ቀላሉን ነገር መረጃ ማቅረብን በተመለከተ የቀረበውን የግብር ይውጣ ሥራ ለማመልከት ስል
ያቀረብኩት ነው ፡፡ ይህችን ሰነድ አሰባስቦ መልክ በማስያዝ ማቅረብ ያቃታችሁ አገርን የመምራት የሚያህል
ኃላፊነት እንዲት ተሸከማችሁ ? እስቲ ደግሞ አስገራሚውንና እርስ በእርሱ የሚጣረሰውን ትንተናቸውን
እንመልከት ፡፡ መኢሶን ለምን እራሱን
ከኢማሌድህ አገለለ ? ለዚህ ጥያቄ ሻምበል ፍቅረሥላሴ የሠጡት መልስ የሚከተለውን ይመስላል ፤ “ የአገራችን ጠላቶች የከፈቱብንን የተቀናበረ ጦርነት በምን ዘዴ እንመክት ? አደጋውንስ እንዴት አድርገን
እናስወግድ ? ብሎ ከመመካከርና ጠንክሮ ከመቆም ይልቅ መኢሶን አብዮቱን በመክዳት ለመሸሽ ውሳኔ
ለማድረግ በመጋቢት ወር 1969 ኮንፈረንስ ጠራ ፡፡ የኮንፈራንሱ ተሳታፊዎች በአገሪቱ ወቅታዊ ሁኔታ ላይ
በስፋት ከተወያዩ በኋላ “ ከደርግ ጋር የመሠረትነው ትብብር ተቋርጧል ፣ የትግል ለውጥም አድርገናል “ የሚል ውሣኔ አሳለፉ ካሉ በኋላ ፤ ከአብዮቱ “የሸሸንበትን” ምክኒያት ግን በሁለት ከፍለው ያቀርቡታል ፡፡ “ አንደኛው ምክኒያት መኢሶን በአቋራጭ በብልጣብልጥነት ሥልጣን በአጭር ጊዜ እጨብጣለሁ ብሎ የቀየሰው
ዘዴ ተግባራዊነት እየራቀ መምጣቱ ፣ ሁለተኛው ምክንያት ደግሞ የመኢሶን መሪ ካድሬዎች ፈሪና ድንጉጥ
መሆናቸው ነው “ በማለት ይደመድማሉ ፡፡ እስቲ የሻምበሉን ግምቶች አንድ ባንድ እንመልከታቸው ፡፡ ይህ
መኢሶን ባቋራጭ በብልጣብልጥነት ለሥልጣን ያበቃኛል ብሎ የቀየሰው ዘዴ ምን ይሆን ? እርሳቸው አዋጁን
ይጠቅሱታል እንጂ አንብበውትም የሚያቁ አይመስለኝም ፡፡ ይህ ገጽ 231 ላይ የጠቀሱትን አዋጅ አንብበውት
ቢሆን ኖሮ ፣ ሥልጣንን በተመለከተ የመኢሶንን ዕቅድ አዋጁ ላይ ያገኙት ነበር ፡፡ አዋጁ የሥልጣን ጥያቄን
በተመለከተ ፤ “ የሠፊው ሕዝብ ትግል ተደራጅቶና ገፍቶ አብዮታዊ ሕዝባዊ ግንባሩ እንደተቋቋመ በትግል
ውስጥ የተሳተፉት የግንባሩ አባል ፓርቲዎችና የፖለቲካ ድርጅቶች ከሚያቀርቧቸው ምልምሎች መሀከል
ሕዝቡ በሙሉ ነፃና ምሥጥራዊ በሆነ ምርጫ እንደራሴዎቹን መርጦ የመንግሥቱን ከፍተኛ ሥልጣን
ወደሚይዘው አብዮታዊ ሸንጎ ይልካል ፡፡ የሕዝቡ ወኪሎች አጥንተው ባፀደቁት ሕገ-መንግሥት መሠረት
የመንግሥቱ መዋቅሮች ፣ ዘርፎችና የሥልጣን ክፍፍሎች ተወስነው በወዝ-አደሩ ፓርቲ መሪነት ሕዝባዊ
ዲሞክራሲያዊ ሪፑብሊክ ይቋቋማል ፡፡ “ ነው የሚለው ፡፡ እንግዲህ ይኼ አዋጅ ገና በ1968 ዓ/ም ለሕዝብ
አብረን ቃል የገባንበት ነበር ፡፡ አዋጁ የመኢሶን የሥልጣን መወጣጫ አቋራጭ መንገድ ሊባልም አይገባም ፡፡ እናንተ ግን በደርግ ውስጥ የነበሩትን ተቀናቃኞቻችሁን በግድያ ካስወገዳችሁ በኋላ ፣ አዋጁን ወደ ጎን በማለት
እኛን የወንጀላችሁ ተባባሪ በማድረግ ሥልጣን ያለሕዝብ ይሁንታ ለመቆናጠጥ ፈለጋችሁ ፡፡ እኛም ከሕዝብ
ጀርባ በሚዶለት ሴራ ተባባሪ አንሆንም በማለታችን ልታጠፉን ተነሳሳችሁ ፡፡ በግልጽ እንገላችኋለን እስከማለት
ደረሳችሁ ፡፡ ያወጣነው አዋጅ ስለሥልጣን ሽግግር የሚለው በሕዝብ ይሁንታ ፤ “በወዝ-አደሩ ፓርቲ መሪነት
ሕዝባዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፑብሊክ ይቋቋማል” እንጂ ፣ ከፍተኛ ወታደራዊ መኮንኖችና ከፍተኛ ሲቪል
ቢሮክራቶች ተባብረው ኢሠፓን ይመሠርታሉ አልነበረም ፡፡ እናንተ ግን ያደረጋችሁት ይኸንኑ ነው ፡፡ አንድ
ፓርቲ ሳይሆን መድበለ ፓርቲ መቋቋም አለበት የተባባልነውንም ሽራችሁ ፣ ሕዝቡም ምርጫ እንዳይኖረው
አንድ ፓርቲ ብቻ ይበቃል በማለት ወሰናችሁ ፡፡ የጉዳችሁ ጉድ ደግሞ ሕዝቡ ከናንተው መሀከል እንኳን
የፈለገውን ግለሰብ እንዳይመርጥ ፣ የአንበሳና የጎሽ ምልክት ያላቸውን ትታችሁ ፣ ዝሆን ምልክት ያለውን
ብቻ ምረጡ አላችሁ ፡፡ ሻምበል ፣ ተዲያ መኢሶን እዝህ ጭምልቅ ውስጥ ለምን አብሮን አልገባም ብለው ነው
“ መኢሶን ከአብዮቱ ሸሸ “ የሚሉን ? ከአብዮቱ የሸሸው የ1968 ቱን አዋጅ የሻረ እንጂ ለአብዮቱ ተግባራዊነት
በፅናት የታገለው መኢሶን ሊሆን አይችልም ፡፡ ለመሆኑ አብዮት ማለት ደርግ ማለት ነው ብሎ የነገሮት
ማነው ? እናንተ የወር ደሞዘተኞች ሆናችሁ የንጉሡን ሥልጣን ስትንከባከቡ ፣ መኢሶን እንደ ፖለቲካ
ድርጅት የንጉሡን ሥርዐት ለመለወጥ ከውስጥም ከውጭም ይታገል እንደነበር አለማወቆን ከመጸሐፎ
ተረድቻለሁ ፡፡ ለእርሶ የፖለቲካ ድርጅቶች የተቋቋሙት በናንተ የግዛት ዘመን ይመስሎታል ፡፡ ሌላው አስቂኝ
ነገር ደግሞ “መኢሶን የሸሸው የሱማሌን ጦር ፈርቶ ነው” ያሉት ነው ፡፡ እርሶ ያለፍርሀት ምንም የሚያውቁትነገር ያለ አይመስለኝም ፡፡ በመጀመሪያ ደረጃ ከየገጠሩ ተመልምሎ የመጣውን የሚሊሺያ ጦር ፣ የመኢሶንን
ያህል በቅርብ የምታውቁት አይመስለኝም ፡፡ የመኢሶን ጓዶች ከምልምል ሠራዊቱ ጋር አብረው በመሠልጠን
ወደ ጦሩ ግንባር ለመዝመት ጥያቄ ባቀረቡ ጊዜ እምቢ ማለታችሁን እረሱት ? እስቲ ስለዚህ ጉዳይ የእርሶው
ድርጅት አባል የነበሩት ገስጥ ተጫኔ ምን እንደሚሉ አብረን እንመልከት ፡፡ ገሥጥ “ነበር” ብለው በሰየሙት
የመጀመሪያው መጸሐፋቸው ገጽ 269 ላይ ፤ “ የሶማሊያን ወረራ ለመመለስ በታጠቅ ጦር ሠፈር እየሰለጠነ
በነበረው ሚሊሻ ሠራዊት ውስጥ ተሳትፎ እንዲኖራቸው የኢማሌድኅ አባል ድርጅቶች የደርግን ፈቃድ ጠየቁ ፡፡ በግልም ሊቀ መንበር መንግሥቱን ተለማመጡ ፡፡ በተለይ መኢሶን ብዙ ወትውቶ ነበር ፡፡ “ ካሉ በኋላ
መኢሶን ፤ “ … አሰርጎ ያስገባቸው ካድሬዎቹም ተመንጥረው ወጡ ፡፡ “ ይላሉ ፡፡ መኢሶን ከሠራዊቱ ጋራ
እንዳይቀላቀል ይከልከል እንጂ ፣ የአብዮታዊ ሰደድ ፣ የወዝ ሊግና የማሌሪድ ካድሬዎች በጦሩ ከምፕ ውስጥ
እንደልባቸው ሲፈነጩበት እንደነበር ገስጥ ተጫኔ በዚሁ ገጽ ላይ ያብራራሉ ፡፡ መኢሶን ከጦሩ ጋር አብሬ
ልዝመት አለ እንጂ ከአገር ጉደይ ሸሽቶ አያውቅም ፡፡ ሻምበል ወደዱም ጠሉም ሀቁ እንግዲህ ይኸው ነው ፡፡ ሥልጣን ከሕዝብ ይሁንታ ውጭ አንፈልግም ማለታችንንም አሌ እንዳይሉ ፣ ይህን በተመለከተ አቶ ተስፋዬ
መኮንን “ ይድረስ ለባለታሪኩ “ ብለው ጥቅምት 1985 ያሳተሙትን መጸሐፋቸውን ገጽ 243ን ይመልከቱ ፡፡ ገስጥ ተጫኔም “ነበር” ብለው በ1996 ዓ/ም ያሳተሙትን መጸሐፍ ገጽ 270 ቢመለከቱ አቶ ተስፋዬ ያሉትን
ነው የሚያረጋግጡት ፡፡ ስለዚህ የራሳችሁን ሥልጣን ባቋራጭ የመያዝ ጉጉት የመኢሶን ዘዴ ነው አትበሉ ፡፡ ለሕዝብ በአዋጅ ቃል የገባችሁትን ያጠፋችሁት እናንተ እንጂ መኢሶን አይደለም ፡፡ ለነገሩ መኢሶን ከመደብ
ባህሪያችሁ በመነሳት ይኸንኑ እንደምታደርጉ ገና በ1968 ዓ/ም ግንቦት 11 ቀን ባወጣው በሰሕድ ቁጥር 40
አማካኝነት ለሕዝብ ፤ “ ጊዜያዊ ወታደራዊ መንግሥት ይህን ፕሮግራም ከሥራ ላይ ሊያውል አይችልም ፡፡ ስለዚህም ደርጉ የቀድሞ ወላዋይነቱን ካስቀረ ፤ የዚህን መለስተኛ አዋጅ ሥራ ላይ መዋል የሚያግዙ
እርምጃዎች በመውሰድ የሠፊውን ሕዝብ ትግል ሊያገለግል ይችላል ፡፡ ሠፊውን ሕዝብ ተክቶ ግን ይህን
ፕሮግራም ከሥራ ላይ ሊያውል አይችልም ፡፡ የዚህ መለስተኛ ፕሮግራም ታሪካዊ ቦታ ለአገራችን ችግሮች
ዛሬውኑ መፍትሔ ስለሚያስገኝ አይደለም ፡፡ ሠፊው ሕዝብ ለነዚህ መፍትሔዎች እራሱ እንዲታገል ለማንቃት
፣ ለማደራጀትና ለማስታጠቅ ምቹ ሁኔታን የሚፈጥር በመሆኑ ነው ፡፡ “ ሲል አስታውቆ ነበር ፡፡ ስለዚህ
ሻምበል የሥልጣን ጥመኝነቱ እናንተን የሚመለከት እንጂ መኢሶንን አይደለም ፡፡ በሁለተኛ ደረጃ ያስቀመጡት
መላ ምቶ ደግሞ እኛ “ከአብዮቱ የሸሸነው” የሱማሌን ጦር ስለፈሩ ነው ነው የሚሉት ፡፡ ሻምበል ምን ነካዎት
? መኢሶኖች እኮ ባዶ እጃችንን “ ታጋይ ይሞታል ፣ ትግል አይሞትም “ እያልን ከፀረ-አብዮተኞች ጋር
እንደታገልን እርሶም ሳያውቁት በመጸሐፎ ውስጥ መስክረውልናል እኮ ፡፡ ከሸሸን ያኔ ነበር የምንሸሸው ፡፡ እስቲ
በመጸሐፎ ገጽ 318 ላይ ስለእኛ ያሉትን ላስታውሶት ፡፡ “ እነዓለማየሁ በደርግ ውስጥ ያካሔዱት ሰላማዊ
መፈንቅለ-መንግሥት በሕዝብ ዘንድ ተቀባይነት ያስገኝልናል ብለው የጠሩት ሕዝባዊ ስብሰባ ተቃራኒ ውጤት
አስገኘ ፡፡ መኢሶን ቀስቅሶ ወደ አደባባይ ላወጣው ሕዝብ አቋሙን ለማሳወቅ ጥሩ አጋጣሚ ስለተፈጠረለት
ተጠቀመበት ፡፡ በቀላሉ የማይታይ ኃይል እንደሆነም አሳየ ፡፡ በአደባባይ የታየው የተቃውሞ እንቅስቃሴ
የነዓላማየሁን ቡድን ሲያሳስብና ስጋት ላይ ሲጥል ሌ/ኮሎኔል መንግሥቱንና ደጋፊዎቻቸውን ያበረታታና የልብ
ልብ የሰጠ ነበር ፡፡ “ ብለው ነው የመሰከሩልን ፡፡ እናንተ ወኔያችሁ በከዳችሁ ወቅት መኢሶን የሕዝብን
ድጋፍ በመተማመን ብቻ ባዶ እጁን ከነዓለማየሁ ኃይሌ ጋር ተጋፍጦ እርሶም እንዳመኑት ስላበረታታናችሁና
የልብ ልብ ስለሠጠናችሁ ፈሪ ይሉናል ፡፡ ምን ያድርጉ እርሶ ማሰብ የሚችሉት ፈሪና ደፋር በሚሉ ቃላቶች
ብቻ ስለሆነ ፣ ስለኛ ጀግንነት ሊመሰክሩ አይችሉም ፡፡ ሻምበል ፣ ” ሌባ እናት ልጇን አታምንም “ ይባላል ፡፡ እርሶም ፍርሀቶ መረን የለቀቀ በመሆኑ የተነሳ እኛም እንደ እርሶ ፈሪ መስለን እንታዮታለን መሰለኝ ፡፡ ፈሪ
መሆኔን በምን አወክ ? ይሉኝ ይሆናል ፡፡ ማን እንደነገረኝ ለማወቅ ብዙም አይጨነቁ እርሶው እራሶ ኖት
በመጸሐፎ ውስጥ ያሰፈሩት፡፡
ሌ/ኮ ፣ መንግሥቱ ኃይለማርያም እርሶን እንደማይተናኮሎት በብዙ አጋጣሚዎች አሳውቀዎታል ፣ እርሶ ግን
ከፈሪነቶ ብዛት የተነሣ አምነዋቸው ሊረጋጉ አልቻሉም ፡፡ ከሚገደሉት ማህል በስህተት እንደተደለደሉና በኮ/ል
ዳንኤል አስፋው አማካኝነት ከሞት እንደተረፉ በመጸሐፎ ተርከውልናል ፡፡ ይህ እንግዲህ እርሶ በሌ/ኮሌኔሉ
በክፉ ዐይን እንደማይታዩ ሊያረጋግጥሎት በተገባ ነበር ፡፡ እርሶ ግን ሊቀመንበሩ ከእልቂቱ የተረፋችሁትን ፣
በአዳራሽ ሰብስበው ስለጉዳዩ ሊያስረዷችሁ በፈለጉ ጊዜ ገና እንደተሸበሩ ነበር ፡፡ አስቲ ሁኔታውን እንዴት
እንደገለጹት ላስታውሶት ፡፡ በመጸሐፎ ገጽ 326 ላይ ፤ “ ሌ/ኮሎኔል መንግሥቱ ወደ አዳራሹ ሲገቡ
ከመቀመጫችን ተነስተን ተቀበልናቸው ፡፡ የተረጋጉ ይመስላሉ ፡፡ ከወትሮው ይበልጥ ተኮሳትረዋል ፡፡ ፊታቸው
አስፈሪ ነው ፡፡ የወሰዱትን እርምጃ ስለምናውቅ ትኩር ብለን ዐይናቸውን የመመልከት ድፍረት አጣን ፡፡ ወዘተ.” ብለው ፍርሀቶ ገደብ የለሽ እንደ ነበር አስረድተውናል ፡፡ እኔ የምለው ፣ አልነካህም ከተባሉ በኋላ
ምንድነው እንደዚህ መንፈሽፈሽ ? ወታደር አይደሉም እንዴ ? እተፋፋመ ውጊያ ውስጥ ቢገቡ ምን ሊውጦትነው ? ሌላው የገረመኝ ነገር ደግሞ ስለ እነ መቶ አለቃ ዓለማየሁ ኃይሌ ማልቀስ የነገሩን ነው ፡፡ ምነው
የእርሶን በአራት ማዕዘን የወረደውን እንባ ዘነጉት ? ያውም መትረፎን ካረጋገጡ በኋላ ፡፡ ሻምበል ፣ መኢሶን
እንደናንተ የለት የለቱን እያሰበ ብቻ የሚጓዝ ድርጅት አልነበረም ፡፡ እናንተ አታነቡም እንጂ ፣ መኢሶን
በትግሉ ወቅት ከአብዮቱ ካፈገፈጋችሁ ጥሏችሁ በሚያመቸው መንገድ እንደሚታገል ቀደም ሲልም ነግሯችሁ
ነበር ፡፡ እናንተ ግን የእኛን ህቡዕ መግባት ከአብዮቱ እንደመሸሽ ቁጠራችሁት እንጂ የትግል ስልት ለውጥ
መሆኑን አልተረዳችሁም ፡፡ መኢሶን የሚከተለውን የትግል ስልት ሚያዚያ 30 ቀን ፣ 1968 ዓ/ም ባወጣው
የሠፊው ሕዝብ ድምፅ ቁጥር 39 ላይ የሚከተለውን ብሎ ነበረ ፤ “ መኢሶን በፕሮግራሙ መግቢያ ላይ
እንደገለጸው ፣ ለነዚህ አበይት ዓላማዎቹና በጠቅላላው ለፕሮግራሙ ሥራ ላይ መዋል … ያለአንዳች
ማወላወል ፤ በምሥጢርና በይፋ ፤ በሕጋዊ መንገድና በሕገ-ወጥነት ፤ በሠላማዊ መንገድና በአመፅ ፤
እንደጊዜውና እንደሁኔታው በሚለወጥ ታክቲክ ፤ ምንም ጊዜና ምንም ሁኔታ በማይለውጠው ቆራጥነትና
ታታሪነት የሚታገሉ አብዮታዊያንን አስተባብሮ ለኢትዮጵያ ሰፊ ሕዝብ ነፃነትና አንድነት አሰልፏል ፡፡ የኢትዮጵያ ጭቁኖች የሚያደርጉትን ትግል ዳር እስከ ዳር አስተባብሮ ፤ የተጣራ አብዮታዊ አመራር ለመስጠት
በጭቁን ሕዝቦችና በታሪክ ፊት የተቀበለውን አደራ እስከ መጨረሻው ይጠብቃል ፡፡ ጭቁኖች በትግላቸው
እንደሚገፉ ፤ በትግል እሳት የተፈተኑ አባሎቹ አብዮታዊ ግዴታቸውን ለመፈጸም ወደኋላ እንደማይሉ ሙሉ
እምነት አለው ፡፡ “ ከዚህ መግለጫ የምንረዳው ነገር ቢኖር ፣ መኢሶን የሶማሌ ጦርነት ከመምጣቱ ቀደም
ብሎም የትግል ስልት ለውጥ ሊያደርግ እንደሚችል ማሳወቁን ነው ፡፡ ስለዚህ የትግል ስልት ለውጥ ማድረጉ
እርሶ እንደሚሉት ድንገተኛና ከፍርሀት ጋር የተያያዘ አልነበረም ማለት ነው ፡፡ በተለይ እናንተ ከጥር 30 ቀን
፣ እሰከ የካቲት 4 ቀን ፣1969 ዓ/ም ድረስ ዝግ ስብሰባ አድርጋችሁ ሌ/ኮሎኔል መንግሥቱን ባለሙሉ
ሥልጣን ከአድርጋችሁ በኋላ ፤ በ1968 ዓ/ም በአዋጅ ለሕዝብ የገባነው ቃል ኪዳን እንደተሻረ ምንም ጥርጥር
አልነበረንም ፡፡ ከዚያ በኋላማ በአገሪቱ ጉዳይ አለኛ ማን አለ በማለት ለያዥ ለገራዥ አስቸግራችሁ ነበር ማለት
ይቻላል ፡፡ የሚገርመው ነገር እኛን ለማጥፋት ከተባበራችሁ በኋላ እርስ በርስ ደግሞ መጨራረሳችሁ ነው ፡፡ እርሶ ግን ለሌ/ኮሎኔል መንግሥቱ ኃይለማርያም ሥልጣን ስጋት ስላልነበሩ ወዳጅ ጓደኞቾ ሲያልቁ ከዚህ ሁሉ
መአት አመለጡ ፡፡ በጦር ሜዳ ውሎ ልምድ የነበራቸውን የጦር መኮንኖች እንድ ባንድ አጠፋችኋቸው ፡፡ መድረክ ላይ የሚሠራ ትያትር ይመስል እነመጋቢ ሃምሣ አለቃ ለገሠን የሠሜን ጦር አዛዥ አድረጋችሁ
ሾማችሁ ላካችሁ ፡፡ አንድም ጥይት ሳይተኩሱ የሠሜን ግንባሩን ጥለው ተመለሱ ፡፡ እኝህ ሰው
በሕይወታቸው የመቶ ጦር እንኳን መርተው አያውቁም ፡፡ ባህር ኃይሉንም ፣ ፖሊስ ሠራዊቱንም በበታች
ሹማምንቶች አስያዛችሁ ፡፡ በዚሁም የከፍተኛ መኮንኖችን ሞራል ገደላችሁ ፡፡ በመጨራሻም አገሪቷን አሁን
ለወደቀችበት ሁኔታ ዳረጋችኋት ፡፡ ይኸው ነው እንግዲህ ሻምበል የናንተ ሥራ ፡፡ እስካሁን የመኢሶንን
አመራር የሚተቹ ግለሰቦች የመኢሶን አመራሮች የወጣላቸው ምሁራን ናቸው ፣ ለአብዮቱም ከፍተኛ አስተዋፆ
ማበርከታቸው አሌ አይባልም ካሉ በኋላ ፣ የሚያዥጎደጉዱት ስድብና ወቀሳ ነው ፡፡ ኢሕአፓና እነመንግሥቱ
ኃይለማርያም መኢሶንን በቅብብሎሽ በመግደልም ፣ በማሰርም ካዳከሙትና ፣ አገሪቷን አሁን ላለችበት ሁኔታ
ከዳረጓት በኋላም የሚወቅሱት መኢሶንን ነው ፡፡ በዚህ ዐይነት በአገራችን ስህተት የሚሠራው ምሁሩ እንጂ
መሀይሙ አይደለም ማለት ነው ፡፡ እኔ እርሶን ብሆን ፣ ይኸንን ሠርቻለሁ ብዬ መፎከር ይቅርና ቀና ብዬም
ሰው አላይም ነበር ፡፡ እርሶ ግን ባለፈው ጥፋቶ የተፀፀቱም አይመስሉም ፡፡ በዚሁ ላብቃ ፡፡

መርዕድ ከበደ

የጎሣ ፖለቲካ፣ የጎሣ ግጭቶች እና መዘዛቸው በኢትዮጵያ (በዘመነ ወያኔ)

$
0
0

(ክፍል አንድ)
ከያሬድ ኃይለማርያም
ብራስልስ፣ ቤልጂየም፤
መግቢያ
ይህ ጽሑፍ በኢትዮጵያ ላለፉት አስርት አመታት ጎሣና ኃይማኖትን መሰረት አድርገው በተደጋጋሚ ጊዜያት በተከሰቱት ግጭቶች ዙሪያ እና ግጭቶቹ ባስከተሉት ሰብአዊና ቁሳዊ ጉዳት ላይ የሚያተኩር ነው። በተለይም ከ1983 ዓ.ም. ወዲህ ጎሣን መሰረት ያደረገውን የኢሕአዴግ ፌዴራላዊ የመንግስት አወቃቀር ተከትሎ በአገሪቱ የተለያዩ ክልሎች ውስጥ የተከሰቱ ዋና ዋና ግጭቶችን ይዳስሣል። ለግጭቶቹ መንስዔ ተደርገው የሚጠቀሱትን ጉዳዮች፣ በግጭቶቹ ሳቢያ በሰው ሕይወትና በሕዝብ ንብረት ላይ የደረሰውን የጉዳት መጠን፣ ግጭቶቹ እንዳይከሰቱ ለመከላከልም ሆነ ከተከሰቱ በኋላም ለማብረድ እና ዘላቂ በሆነ መልኩ ለመፍታት በመንግስት የተወሰዱ እርምጃዎች፣ የመንግስት የግጭቶች አፈታት ስልት፣ እና ሌሎች ተዛማጅ ጉዳዮችን ይህ ጽሑፍ በመጠኑ ይዳስሳል።
የጽሑፉም ዋነኛ ዓላማ ጎሣን እና ኃይማኖትን መሠረት አድርገው የሚቀሰቀሱ ግጭቶች፤ ሰብአዊ መብቶች በገፍ በሚጣሱበት፣ ዴሞክራሲያዊ መብቶችና ነፃነቶች በማይከበሩበት እና የሕግ ልዕልና ባልተረጋገጠበት፤ እንዲሁም ነፃና ገለልተኛ የፍትሕ ተቋማት በሌሉበት እንደ ኢትዮጵያ ባለ አገር ውስጥ የሚኖራቸውን መጥፎ ገጽታ ማሳየት ነው። በተለይም የኢሕአዴግን የጎሣ ፖለቲካ አወቃቀር ተከትሎ በአገራችን ተደጋግመው በመከሰት ላይ ያሉት የጎሣ ግጭቶች በአገሪቱ የልማት እንቅስቃሴዎችና በሕዝቡ ሰላምና ደኅንነት ላይ የሚያስከትሉትን ኢኮኖሚያዊ፣ ፖለቲካዊ እና ማኅበራዊ ቀውሶች ማመላከት ነው።
ወደዚህ ጽሑፍ ዋና ክፍል ከመግባቴ በፊት ለአንባቢዎቼ ከላይ ከገለጽኳቸው የጽሑፉ አላማዎች በተጭማሪ የተወሰኑ ነገሮችን ከግምት ውስጥ እንድታስገቡልኝ ለማሳሰብ እወዳለሁ። በመጀመሪያ ይህን ጽሑፍ ለማዘጋጀት ምክንትያት የሆነኝን ነገር ልግለጽ። ለስምንት አመታት በሰብአዊ መብት ጥሰቶች አጣሪነት በኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ጉባኤ (ኢሰመጉ) ውስጥ ተቀጥሬ ባገለገልኩበት ዘመን ድርጅቱ ተከታትሎና አጣርቶ መግለጫ ባወጣባቸው በርካታ የጎሣና የኃይማኖት ግጭቶች ውስጥ በምርመራ ሥራ ተሳትፌአለሁ:: የተወሰኑትን ግጭቶች ከሌሎች የሥራ ባልደረቦቼ ጋር በመሆን ሥፍራዎቹ ድረስ በመገኘት፤ የተቀሩትን ደግሞ ሌሎቹ የድርጅቱ የምርመራ ሠራተኞች፤ በአካል ተገኝተው ካሰባሰቡዋቸው መረጃዎች በመነሳት ያካፈሉኝን እውቀትና መረጃ በመንተራስ ነው። ለዚህም ጽሑፍ በዋነኛነት ኢሰመጉ በግጭቶቹ ዙሪያ የወጣቸውን መግለጫዎች በማጣቀሻነት እጠቀማለሁ። እንዲሁም ሌሎች አለም አቀፍ የሰብአዊ መብት ድርጅቶች ያወጡዋቸውን መግለጫዎችና ሰነዶች በአባሪነት እጠቅሳለሁ።
ይህ ጽሑፍ ሦስት ክፍሎች ሲኖሩት፤ በመጀመሪያው ክፍል በጎሰኝነት ስሜት ላይ የተመሰረተ የፖለቲካ አደረጃጀት እና አስተሳሰብ፣ የጎሣ ግጭቶች እና ከሰብአዊ መብቶች አጠባበቅ ጋር ያላቸውን ግኝኙነት በተመለከተ አለም አቀፍ ድንጋጌዎችን እና ሌሎች ሰነደችን በማጣቀስ የሚዳሰስበት ክፍል ነው። የዚህ ክፍል አላማም በኢትዮጵያ ውስጥ እየታየ ያለውን የጎሠኝነት ስሜትና እያስከተለ ያለውን ግጭት ባህሪይ እና አካሄድ በቅጡ ለመረዳት ይረዳ ዘንድ መሰረታዊ በሆኑ ጠቅላላ አስተሳሰቦችና በሌላው የአለም ክፍልም ይህ አይነቱ ችግር ያለውን ገጽታ በመጠኑ የሚዳስስ ነው። ሁለተኛው ክፍል በኢትዮጵያ ውስጥ በተደጋጋሚ ስለተከሰቱትና እየተከሰቱ ባሉት ግጭቶች ላይ የሚያተኩር ነው። በዚህ ክፍልም ውስጥ ኢትዮጵያ ውስጥ የተከሰቱትን ግጭቶች ባህሪ፣ መንሰዔያቸውን፣ የደረሱትን ጉዳቶች፣ የመንግስትን ሚና እና ሌሎች ተዛማጅ ጉዳዮች ላይ ያነጣጠረ ነው። የመጨረሻውና ሦስተኛው ክፍል የኢሕአዴግ መንግስት የሚከተለው ፖሊሲ፣ ያወጣቸው ሕጎች፣ ግጭቶችን ቀድሞ እንዳይከሰቱ የመከላከልና ሲከሰቱም በቀላሉ ተቆጠጥሮ ዘለቄታዊ መፍትሔ የመስጠቱ ሂደት ምን እንደሚመስል በመጠኑ የሚፈትሽ ነው።

I. ጎሠኝነት፣ የጎሣ ግጭቶች እና ሰብአዊ መብቶች
1.1. ጎሠኝነት
የሰው ልጆች ሁሉ በሰብአዊ ፍጡርነታቸው ክቡር መሆናቸውን፤ እንዲሁም እኩልና ሊነጣጠሉ የማይችሉ መብቶች እና ነፃነቶች ያሏቸው መሆኑን በአለም አቀፍ ድንጋጌዎች ላይ ሰፍሯል። የእነኚህ መብቶች እና ነፃነቶች በአግባቡ መረጋገጥና መከበር ለአለም ሰላም እና ለሕዝቦች ደኅንነት ዋነኛ ምሰሶም እንደሆነ ተገልጿል። የሰው ልጆች በሰብአዊ ፍጡርነታቸው ተገቢውን ክብር በማያገኙበት፣ ሰው በመሆናቸው ብቻ የተጎናጸፉዋቸው መብቶች እና ነፃነቶቻቸው ባልተረጋገጠበት እና በገፍ በሚጣሱበት ሥፍራዎች ሁሉ አይነታቸውና ደረጃቸው ይለያይ እንጂ ግጭቶች፤ ከፍ ሲልም ጦርነቶች ይከሰታሉ። በመላው አለም መብቶቻቸው የተረገጡባቸውና ሰብአዊ ክብርን የተነፈጉ ሰዎች ለነፃነቶቻቸው መረጋገጥ እና ከጨቋኞቻቸው ነፃ ለመውጣት የሚያደርጉትን ትግል ተከትሎ በርካታ ጦርነቶች እና ግጭቶች በአለም ተከስተዋል፤ አሁንም በተለያዩ ሥፍራዎች ይታያሉ። አለማችን እጅግ ዘግናኝ የሆኑ እና በሚሊዮኞች ለሚቆጠሩ የሰው ልጆች መጥፋት ምክንያት የሆኑ በዘር ጥላቻና በጎሠኝነት ስሜት የተቀጣጠሉ በርካታ ግጭቶችን እና ጦርነቶችን አስተናግዳለች።
የተባበሩት መንግስታት ባወጣቸው የተለያዩ ሰነዶች ላይ እንደተጠቆመው ድርጅቱ ከተቋቋመበት፣ እ.ኤ.አ. ከ1945 ወዲህ እንኳን ከተከሰቱት በርካታ ጦርነቶች ውስጥ ዐብይ በሚባሉት ከመቶ በላይ በሆኑ ትላልቅ ጦርነቶች ብቻ ከ20 ሚሊዮን በላይ ሰዎች ሞተዋል። በአሥር ሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ደግሞ በጦርነቶቹ ሳቢያ ለስደት፣ ለርሃብ፣ ለድህነት እና ለበሽታ ተዳርገዋል። አብዛኛዎቹ ግጭቶች የዘር ልዩነትን መነሻ ባደረጉ ውጥረቶች፣ ያመረረ እና ጽንፍ የያዘ ብሔራዊ ስሜትና አክራሪ ጎሠኝነትን ተከትለው የተቀሰቀሱ ናቸው። አንዳንድ ጥናቶች እንደሚያመላክቱት ከሆነ ከሁለተኛው የአለም ጦርነት ወዲህ በመላው አለም በፖለቲካ ብጥብጥ ሳቢያ ከሚሞቱ ሰዎች መካከል 80 በመቶ የሚጠጉት በጎሣ ግጭቶች ምክንያት ነው። በአለም ታሪክ ውስጥ ጎላ ብለው ከሚጠቀሱት ግጭቶች መካከል በአይሁዳዊያን ላይ የደረሰው ስቃይና የጅምላ ጭፍጨፋ፣ በጂፕሲዎችና በሶዶማዊያን ላይ የተካሄደው እልቂት፣ በሩሲያ እስታሊን በሰው ዘር ላይ የፈጸመው አሰቃቂ ወንጀል፣ በደቡብ አፍሪካ የአፓርታይድ ሥርዓት፤ እንዲሁም በዚምባብዌና በናሚቢያ ንኡሳን ነጮች (አውሮፓዊያን) የፈጸሙዋቸው እልቂት፣ በላይቤሪያ፣ በሩዋንዳ፣ በሱዳን፣ በሱማሌ እና በሌሎች የአፍሪካ አገሮች በተከሰቱ የእርስ በርስ ግጭቶች ሳቢያ ሚሊዮኖች ያለቁባቸውን ሁኔታዎች መዳሰስ እንችላለን።
በመጀመሪያ ደረጃ በጎሣ (ethnicity) እና በዘር (racial) ማንነት መካከል ያለውን ልዩነትና ዝምድና በመጠኑ ለመዳሰስ እወዳለሁ። የጎሠኝነት ስሜትና ማንነት የሚመነጨውና የሚጎለብተው እያንዳንዱ ሰው እራሱን ከአንድ በቋንቋ፣ በባሕል፣ በአካባቢያዊ ሁኔታ፣ ልማዶች እና ሌሎች ማኅበራዊ ጉዳዮች ዙሪያ ከተሳሰረ የዘር ግንድ ጋር መነሻ በማድረግ የተደራጀ ወይም የተሰባሰበ የኅብረተሰብ ክፍል አባል አድርጎ ሲቆጥር እና በእነዚሁም መስፈርቶች እራሱን ከሌሎች የኅብረተሰብ ክፍሎች የተለየሁ ነኝ ብሎ ማሰብ ሲጀምር ነው። በዘር ላይ የተመሰረተው ማነነት በርካታ ጎሣዎችን በውስጡ ያቀፈ ሲሆን ተመሳሳይ የሆነ ተፈጥሮአዊ የሆነ አካላዊ መገለጫዎችን መሰረት በማድረግ የቡድንኑ አባላት እራሳቸውን ከሌሎች ለይተው የሚገልጹበት ወይም በሌሎች ዘንድ የተለዩ የተርገው የሚገለጹበት ሁኔታ ነው፡፡ ይህ አይነቱ የቡድን ዘር መገለጫ በሥነ-ተፈጥሮ ሳይንስ የተደገፈ ሳይሆን ለቡድኑ
Ethnicity, conversely, is defined as a sense of common ancestry based on cultural attachments, past linguistic heritage, religious affiliations, claimed kinship, or some physical traits (1998, 19)፡ http://stanford.library.usyd.edu.au/entries/race/#RacVerEth
Racial identities are typically thought of as encompassing multiple ethnic identities (Cornell and Hartmann

መገለጫ በሚሰጠው ሰው አስተሳሰብና ምርጫ ላይ የተመሰረተ ነው። በሁለቱ መካከል ያለው ትልቁ ልዩነት የጎሣ ማንነት በእያንዳንዱ የጎሣው አባል መርጫና ፍላጎት ላይ የተመሰረተ ነው። አንድ ሰው የአንድን ጎሣ ባህል፣ ቋንቋ፣ ልማዶች እና ሌሎች መገለጫዎችን ወዶና ፈቅዶ ሲያደርጋቸውና እራሱ የዛ ጎሣ አባል አድርጎ ሲቆጥር ነው የማንነቱ መገለጫ የሚሆነው። የዘር ማንነት መገለጫ ግን በእያንዳንዱ ሰው ፍላጎትና ምርጫ ሳይሆን በሌሎች አካላት ውሳኔ የሚጫን ነው። ለጥቁሮች መገለጫ የተደረገውን negro የሚለውን አገላለጽ የወሰንድ እንደሆነ በነጭ አክራሪዎች በመላው አለም ጥቁር የቆዳ ቀለም ላላቸው የሰው ልጆች ሁሉ የሰጡት መጠሪያ ነው።
የጎሣ ማንነት ቋንቋን፣ ባህልን፣ ኃይማኖታዊ ሥርዓቶችን ለማስተዋወቅ፣ ለማበልጸግ እና ይዞ በማቆየትም ከትውልድ ትውልድ እንዲተላለፉ ለማድረግ በመነጨ ፍላጎት ላይ ብቻ ሲወሰን እና ከዚህ አልፎ ለፖለቲካ ፍጆታ ሲውል የሚኖረው ውጤት እና ገጽታ ፍጹም የተለያየ ነው። በመጀመሪያው የአስተሳሰብ መስመር ላይ የተመሰረተው የጎሣ ማንነት ልዩነቶችን አጉልቶ በማውጣት ለመናቆሪያ ሳይሆን እንደ ጥለት ክር የተጠላለፉት የእያንዳንዱ የኅብረተሰብ ክፍል ባህሎች፣ ቋንቋዎች፣ ኃይማኖታዊ እና ታሪካዊ ትውፊቶች ለጠቅላላው ማኅበረሰብ የጥንካሬ እና ኅብረ ውበት ምንጮች ተደርገው ነው የሚቆጠሩት። በዚህ አይነቱ ማኅበረሰብ ውስጥ የአንዱ ክፍል ቋንቋ፣ ባህልና ሌሎች ማኅብራዊ እሴቶች ሁሉ የሌሎቹ የኅብረተሰብ ክፍሎች ሃብትና ጌጦች ናቸው። አንዱ ያለሌሎቹ፤ ሌሎቹም ያለአንዱ ውበትና ጥንካሬ የላቸውም። ይህ አይነቱ ማኅበረሰብ በውስጡ ግጭቶችና ቅራኔዎች ባያጡትም አንዱ የሌላውን ዘር ከምድረ ገጽ ለማጥፋት በመነሳት ወደሚፈጸሙ ዘግናኝ እልቂቶች አያመሩም። ልክ በአንድ ቤተሰብ አባላት መካከል ግጭቶች ተነስተው በእርቅ እንደሚፈቱት ሁሉ በዚህ አይነቱ ማኅበረሰብ ውስጥም የሚነሱ ቅራኔዎችና አለመግባባቶች በየአገሩ ወግና ባህል ወይም በሕግ አግባብ አፋጣኝ መፍትሄ ሲለሚያገኙ ወደ እልቂት አያመሩም።
ሁለተኛውና ለፖለቲካ ግብ ማሳለጫ መንገድ ተደርጎ የሚወሰደው ጎሣን መሰረት ያደረገው የማንነት መገለጫ እና የኅብረተሰብ ክፍሎች መቧደን ከላይ ከተጠቀሰው የጎሣ ምልከታ ጋር ከሚጋራው አንድ ነገር ውጪ እጅግ የተለየ መልክ እና ይዘት ያለው ነው። ሁለቱም የጎሣ ምልከታዎች መነሻቸው አንድ ነው። ይህውም በአንድ ማኅበረሰብ ውስጥ በቋንቋ ወይም በባህል ወይም በኃይማኖት ወይም በሌሎች የማንነት መገለጫ ተደረገው በልማድ በሚወሰዱ ልዩነቶች ዙሪያ የተሰባሰቡ የኅበረተሰብ ክፍሎች መኖራቸው ነው። አንድ ወጥ የሆነ ቋንቋ፣ ባህል፣ ኃይማኖትና ታሪክ ባለው ማኀበረሰብ መካከል የተለያየ የኅብረተሰብ ደረጃዎችና ክፍሎች ቢኖሩም የጎሣና የጎሠኝነት ጎዳዮች ጭርሱኑ የሚታሰብ ነገሮች አይደሉም። የጎሣ ልዩነቶች ከኅብር ውበት መገለጫነትና ባህልን፣ ቋንቋን፣ ታሪክን እና ኃይማኖታዊ እሴቶችን ለማስተዋወቅና ለማዳበር ከሚኖረው ፋይዳ ባለፈ የፖለቲካ አስተሳሰቦች ማቀንቀኛ እና የፖለቲከኞች የመታገያ መሳሪያ መሆን ሲጀምር ውበቱ ይደበዝዛል ወይም ጭርሱኑ ይጠፋል። ጎሠኝነት ፖለቲካዊ ገጽታው እጅግ ተጋኖና ጎሎቶ በወጣ ቁጥር ያንን ማኅብረተሰብ አቆራኝተው እና አፋቅረው ያቆዩትን ሠንሰለቶች የመበጣጠስ ኃይል አለው። በጎሣ በተሰበጣጠረው የኅብረተሰብ ክፍል ውስጥ የሚኖረው አወንታዊ ሚና ይቀርና የልዩነት ግንብ ይሆናል። የእያንዳንዱ ጎሣ ቋንቋ፣ ባህል፣ ታሪክና ኃይማኖታዊ እሴቶች የራሱ ብቻ ይሆናሉ። አንዱ የሌላው ውበትና የጥንካሬ ምንጭ መሆኑ ይቀርና በፉክክርና በመበላለጥ ስሜት ላይ የተመሰረተ ልዩነት ይፈጥራል። ከዚያም አልፎ በጠላትነት የመተያየት ስሜት ይመነጫል። እያንዳንዱ ጎሣም በልዩነት ግንብ ውስጥ የራሱን ደሴት ይመሰርታል። በእንዲህ አይነቱ ማኅበረሰብ ውስጥ የሚፈጠረው ጎሣን መሰረት ያደረገ ቅራኔ ሁለት መልክ ይይዛል።
የመጀመሪያው በእያንዳንዱ የጎሣ ክፍል ውስጥ ፖለቲካዊ ይዘት ያለው ፉክክርና ግብግብ ጥላቻን ይወልድና ወደ አካላዊ ግጭትም ያመራል። ጎሠኝነት ከዘረኝነት ጋር የተዛመደ እንደመሆኑም የጎሠኝነት ስሜት የሚመነጨውና የሚጎለብተው እያንዳንዱ ሰው የኔ የሚለው የዘር ሀረግ ወይም ጎሣው ከሌሎች ሰዎች ዘር ወይም ጎሣ የተሻለ ወይም የበለጠ ነው ብሎ ማሰብ ሲጀምር ነው። ይህ አይነቱ አስተሳሰብም ሰዎች ሁሉ በፈጣሪያቸው ፊት እኩል እንደሆኑ የሚገልጸውን ኃይማኖታዊ አስተሳሰብ የሚቃረንና ይህንኑ መሰረት በማድረግም “ሰዎች ሁሉ እኩል ክብርና መብቶች ይዘው ነፃ ሆነው ተፈጥረዋል። የማሰብና የማመዛዘን ችሎታ በተፈጥሮ ስለታደሉ እርስ በርሳቸው በወንድማማችነት መንፈስ ሊተያዩ ይገባል።” በማለት የሚደነግገውን የሰብአዊ መብቶች ዓለም አቀፍ ቃል ኪዳን አንቀጽ 1 የሚጥስ ነው።
ሁለተኛው ግጭት ደግሞ በእያንዳንዱ የጎሣ ቡድን ወስጥ የሚፈጠረው የግለኝነትና ጤናማ ያልሆነ የመበላለጥ ስሜት ሁሉንም የኅብረተሰብ ክፍሎች አንድ አድርገው ይዘው ያቆዩትን ታሪካዊ እና ሌሎች አገራዊ መገለጫዎች ይንዳል፤ እንዲሁም የጋራ ጥቅምን ማስከበሪያ የሆነውን ሕገ-መንግስታዊ ሥርዓትን ያናጋል። አልፎ ተርፎም አገርን እስከማፍረስ የሚዘልቅ ችግርን ያስከትላል። በዚህ አይነቱ ችግር ምክንያት በርካታ ትላልቅ አገሮችች ፈርሰው በጎሠኞች ደሴቶች ተቀይረዋል። የጎሠኝነት ስሜት በጠነከረና አብጦ በወጣ ቁጥር አገራዊ ስሜት ይከስማል፣ የአብሮነት ታሪክ ይዘነጋል፣ ጠባብነትና ጎጠኝነት ይነግሳሉ። እዚህ ደረጃ ላይ የደረሰ ማኅበረሰብ በበቀልና በጥላቻ ስሜት ተወጥሮ ስለሚቆይ የእልቂት አፋፍ ላይ ነው የሚቆየው። ተያይዞ ለመጥፋትና ቁልቁል መቀመቅ ለመውረድ ትንሽ ነገር ይበቃዋል። በሩዋንዳና በሌሎች የአለማችን ክፍሎች አስከፊ በሆነ መልኩ የተፈጸሙት የዘር ማጥፋት ወንጀሎች ምንጫቸው ይሄው ነው።
በአለም አቀፍ ደረጃ የተደረጉ አንዳንድ ጥናቶች እንደሚያሳዩት ጎሠኝነትን ወይም የጎሣ-ብሔረተኝነትን መነሻ ያደረጉ ግጭቶች ባህሪያቸው እና መገለጫቸው የተለያየ ነው። ጥቂቶቹን ለመዳሰስ ያህል፤ የፖለቲካ ሥልጣንን በማዕከላዊነት በያዘ የኅብረተሰብ ክፍል እና ከፖለቲካ ምህዳሩ ተገልሎ የዳር ተመልካች እንዲሆን በተደረገ የኅብረተሰብ ክፍል ማካከል ያለውን ቅራኔ መሰረት ያደረገው የጎሣ ግጭት አንዱና በዋነኝነት የሚጠቀሰው ነው። ሁለተኛው ደግሞ በብሄር ምንጫቸው ምክንያት ወይም በቆዳ ቀለማቸው ወይም በሚከተሉት እምነት ወይም በኃይማኖታቸው ወይም በሌሎች ምክንያቶች የተነሳ በእኩልነት የመኖር መብታቸውን እና መሰረታው መብቶቻቸውን በተነፈጉ እና ጥላቻን መሰረት ላደረገ መድልዎ እና ጥቃት የተጋለጡ የኅብረተሰብ ክፍሎች የሚያነሱትን ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ የእኩልነት ጥያቄዎችን ተከትሎ የሚቀሰቀሰው የጎሣ ግጭት ነው። ሦስተኛው ደግሞ፤ በሚኖሩበት ማኅበረሰብ ውስጥ ተገቢውን የፖለቲካ እና ኢኮኖሚያዊ ድርሻ ተነፍገናል ወይም የሚገባንንን ያህል አላገኘንም የሚል ጥያቄን መነሻ በማድረግ ከሌላው ማኅበረሰብ ተገንጥዮ የራሴን አገር እና ግዛት እመሰርታለው የሚሉ ኃይሎች የሚያነሱትን ጥያቄ መነሻ አድርጎ ከሌላው የኅብረተሰብ ክፍል ጋር የሚደረገ ግጭት ነው። አራተኛው የጎሣ ግጭት ደግሞ በአንድ ግዛት ውስጥ ሁለት ወይም ከዚያ በላይ በሆኑ የጎሣ ቡድኖች መካከል የኢኮኖሚና የፖለቲካውን የበላይነት ለመቆናጣጠርና የማዕከላዊውን መንግሥት ሥልጣን በበላይነት ለመቆጣጠር የሚደረጉ ፉክክሮችን ተከትሎ በሚፈጠር አለመግባባት የሚቀሰቀስ ግጭት ነው።
ከላይ የተጠቀሱት የጎሣ ግጭቶችና መንሰዔዎቻቸው በግልጽ እንዲሚያሳዩት ጎሠኝነትን መሠረት ያደረጉ የማንነት መገለጫዎች የፖለቲካ ግብ ማሳኪያ ሲሆኑ መድረሻቸው ጥላቻና ሌሎችን ‘የእኛ ጎሣ አካል አይደሉም’ የሚሉዋቸውን የኅብረተሰብ ክፍሎች ማግለልና ሲከፋም ዘራቸውን ከምድረ-ገጽ ለማጥፋት እስከ መሞከር ይዘልቃል። ይህ ችግር የተከሰተው እንደ ኢትዮጵያ ባለ እጅግ በተሰበጣጠረ ማኅበረሰብ ውስጥ ሲሆን የዘረኝነት መርዙ በብዙ መንገዶች ሊንጸባረቃ ይችላል። በልማት እንቅሳቅሴ፣ በትምህርት ዘርፍ፣ በኢኮኖሚና የንግድ ዘርፍ፣ በመሬት አጠቃቀም ፖሊሲ፣ በግብር አከፋፈል ሥርዓት፤ እንዲሁም በተለያዩ አስተዳደራዊ ዘርፎች ሁሉ የጎሠኝነቱ ስሜትና ውጤቱ በግልጽ ይስተዋላል። ለምሳሌ በፊሊጲንስ ቅጥ አጥቶ የነበረው ጎሠኝነት በአገሪቱ የኃይድሮ ኤሌክትሪክ ኃይል አጠቃቀም ላይ ጭምር በግልጽ ይስተዋል ነበር። በማሌዢያ እና በታንዛኒያ ደግሞ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርት አቅርቦት ላይ የጎሣ መድልዎ አፍጥጦ ይታይ ነበር። በሌሎች አገሮችም የተለያዩ መገለጫዎች ያላቸው ጎሠኝነትን መሰረት ያደረጉ ክፍፍሎችና መድልዎች ተስተውለዋል፤ አስከፊ ግጭቶችንም አስከትለዋል።
በጎሣ የሚደራጁ የፖለቲካ ፓርቲዎች መነሻቸው ከሁለት ክስተቶች የሚመነጭ ነው። የመጀመሪያው ውስጣዊ ምክንያት ነው። ይኽውም በእያንዳንዱ የጎሣ ክፍል ውስጥ ካለው ማኅበረሰብ ከራሱ የሚመነጭ ነው። የአንድ ጎሣ አባላት ኢኮኖሚያዊ፣ ማኅበራዊና ፓለቲካዊ ጥቅማቸውን በተሻለ ሁኔታ ለማስጠበቅ ሲሉ በፖለቲካ የሚደራጁበት ሁኔታ ነው። ሁለተኛው ደግሞ ውጫዊ ምክንያት ነው። ይኽውም የአንድ ጎሣ አባላት በተደጋጋሚ ከአንድ ወይም ከሌሎች ጎሣዎች ጥቃት ሲደርስባቸው፣ ከሌሎች ጎሣዎች በተለየ መልኩ መድሎና መገለል ሲደርስባቸው፣ ከኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ጥቅሞችና ተሳትፎዎች እንዲገለሉ ሲደረግ እና በሌሎች ተመሳሳይ ምክንያቶች አደጋ ሲጋረጥባቸው ይህን መሰሉን ጥቃት ለመከላከል በሚል አካባቢው በፈጠረባቸው አስገዳጅ ሁኔታ በመነሳት የጎሣቸውን አባላት ጥቅም እና ደኅንነት ለማስጠበቅ በማሰብ በፖለቲካ የሚደራጁበት ሁኔታ ነው። በመሆኑም ጎሣን መሰረት አድርገው የሚመሰረቱ የፖለቲካ ፓርቲዎች ድጋፍ የሚያገኙት እንወክለዋልን ከሚሉት የኅብረተሰብ ክፍል ብቻ ስለሆነ የሚታገሉትም ሆነ ሥልጣን ሲቆናጠጡ ቅድሚያ ተጠቃሚ የሚያደርጉት የደገፋቸውን እና የሚወክሉትን የጎሣ ክፍል ብቻ ነው። ጎሣን መሰረት ያደረጉ የፖለቲካ ፓርቲዎች ከጠቅላላው ማኅበረሰብ ጥቅም አንፃር እጅግ ጠባብ የሆነ የቡድን ፍላጎትና አጀንዳን ነው የፖለቲካ ግብ አድርገው የሚነሱት። እነዚህ ኃይሎች የፖለቲካውን ሥልጣን በተቆናጠጡበት ሥፍራ ሁሉ ታዲያ የእኛ ከሚሉት ጎሣ ክፍል በተነጻጻሪ ባለው ቀሪው የኅብረተሰብ ክፍል መካከል ግልጽ የሆነ የጥቅምና የመብት መበላለጥን ይፈጥራሉ። ይህ ሁኔታም እያደር ቅራኔንና ጥላቻን ያራባል።
የጎሠኝነት ስሜት አብጦ በወጣበትና ድርጅታዊ ቅርጽ ይዞ በጎለበተበት አገር ሁሉ የፖለቲካ እንቅስቃሴዎችና አስተሳሰቦች የሚመዘኑትና የሚመነዘሩት በእያንዳንዱ ጎሣ መስፈርት ነው። የፖለቲካ ፓርቲዎችም የሚደራጁትና የሚታገሉት ጎሣዎችን መሰረት በማድረግ ነው። የጎሠኝነት ስሜት ገኖ በሚታይበት ሥፍራ ሁሉ ሰብአዊ መብቶችን ችላ ማለት፣ አሰቃቂ የሆኑ የመብት ጥሰቶችን በሌሎች ላይ መፈጸምና ሰዎችን በፍርሃትና በከፋ ችግር ውስጥ መጣል የተለመዱ ተግባራት ናቸው። ይህ አይነቱ ሁኔታ እጅግ በተከፋፈለ ማኅበረሰብ ውስጥ ሲከሰትና ፓርቲዎችም የጎሣን መስመር ተከትለው መደራጀት ሲጀምሩ ጠንካራ የፖለቲካ ተፎካካሪ ኃይሎች መሆናቸው ጥያቄ ውስጥ ይወድቃል። ምክንያቱም ድጋፍ የሚያገኙት ከሚወክሉት ጎሣ አባላት ብቻ ስለሆነ። ከዚህም ባሻገር ለጠቅላላው ሕዝብ ጥቅም የሚቆሙ ብሔራዊ የፖለቲካ ኃይሎች እንዲዳከከሙ እና እንዲጠፉም ምክንያት ይሆናል። ለዚህም ኢትዮጵያን ጨምሮ በርካታ የአፍሪካ፣ ኢስያ እና ካረቢያን አገራት ዛሬ የሚገኙበትን ሁኔታ ማጤን በቂ ነው። በዚህ መጠነኛ የዳሰሳ ጽሁፍ ውስጥ የጎሠኝነተን አስተሳሰብ፣ መሰረታዊ እና ታሪካው ምንጭ እንዲሁም በጎሣ ግጭቶች ዙሪያ የሚነሱ የተለያዩ ሃሳቦችን ሁሉ ለማካተትም ሆነ በመጠኑም እንኳን ለመቃኘት አይቻልም። እራሱን የቻለ ሰፊ ጥናትና ምርምር የሚጠይቅ ስለሆነ ይህ ዳሰሳ ለዚህ ጽሁፍ ቀጣይ ክፍሎች እንደ መንደርደሪያ ተደርጎ እንዲወሰድ ለማሳሰብ እወዳለሁ።

በቀጣዩ ክፍል እስከምንገናኝ በቸር እንሰንብት።
ያሬድ ኃይለማርያም

http://humanrightsinethiopia.wordpress.com/


ኢህአዴግ 42 ዓመት መግዛትን አስቧል?

$
0
0

ሳሙኤል ተወልደ በርሔ/ሃርስታድ ኖርዌይ/

ሳሙኤል ተወልደ በርሔ/ሃርስታድ ኖርዌይ

ሳሙኤል ተወልደ በርሔ/ሃርስታድ ኖርዌይ


ዛሬ በዓለማችን ላይ በርካታ የሆኑ ለውጦች ተፈጥረዋል፡፡ ህዝብ ይመረጣል፣ ህዝብ ያወርዳል፡፡ ሥልጣን እርስት አይደለም፡፡ የዚህ አይነቱነገር ደግሞ በከፍተኛ ሁኔታ እየሰላ መጥቷል፡፡ ልክ እንደዚህ አይነቱ ሁኔታ በሚታይበት ሁኔታ ደግሞ በተቀራኒው ሥልጣንን የሙጥኝ ብለው ዘላለማዊ አገዛዝን ለመግዛት የሚያስቡ መኖራቸው አልቀረም፡፡ የጠ/ሚ/ር ኃ/ማርያም ደሳለኝ አማካሪ በመሆን የተሾሙ አቶ በረከት ስምኦን ባለፈው ሰሞን “ኢህአዴግ የጀመረውን የልማት ሥራ ለመጀመር በቀጣይነት 42 ወይም 45 ዓመታት ያፈጅበታል” ሲሉ ገለጹ፡፡ ይህ የአቶ በረከት ስምኦን ንግግር ምናልባትም በምርጫ ዋዜማ ሠሞን የተነገረ ከመሆኑ አንፃር ብዙ ነገር እንዲታሰብ ያደርጋል፡፡ ሁልጊዜም ቢሆን ምርጫ በደረሰ ቁጥር በኢህአዴግ ውስጥ ስልት አለ፡፡ የአሸናፊነት መንፈስን በማሰብ ሳይሆን፣ ሁልጊዜም ቢሆን ተሸናፊነትን እያሰበ ይወጣል፡፡ በዚህ ወቅት ደግሞ የተለያዩ ሕጐችንና ደንቦችን በማውጣት ምርጫው ሕጋዊ ወይም ተገቢ ያልሆነ መንፈስ እንዳይኖረው ያደርጋል፡፡ ታዲያ አቶ በረከት ስምኦን እንደሚሉት ሆነ ወይም በቀጥታ ትርጓሜው ሳይሆን፣ በኢህአዴግኛው ትርጓሜው ‹‹በቀጣይም እቺን አገር የምንስተናገደው እኛ ነን›› የሚል መንፈስ ያለው ነው፡፡

ኢህአዴግ በሃገሪቱ በሶስት አይነት ዘርፍ የልማት ሥራ ጀምሯል፡፡ የህዳሴው ግድብ፣ የባቡር ሃዲድ ዝርጋታ እና በንግድ፡፡ እነዚህ ሶስት ሥራዎች ግን ከፍተኛ ገንዘብ የሚጠይቁ ከመሆናቸው አንፃር በተፈለገው መንገድ ተፋጥነው ሊያልቁ የሚችሉ አይደሉም፡፡ ይህ አለመሆኑ ደግሞ ምናልባትም ኢህአዴግ እንደ አቶ በረከት ስምኦን አባባል በፕሮፓጋንዳ ፍጆታ ለመጠቀም ያስቀመጠውም የሚመስልበት ሁኔታ አለ፡፡ የኢህአዴግ ያለፉት 22 ዓመታት ጉዞ ምናልባትም እርሱ ‹‹ዕድገት›› ይበለው እንጂ፣ በብዙ መልኩ ውድቀቶችና ድህነቶች የበዙበት ነው፡፡

የ11 በመቶ ዕድገት ለሌሎች ሳይሆን፣ ለኢህአዴግ ብቻ የሚገለጽ ነው፡፡ የህንጻ መብዛት ‹‹የሃገር ዕድገት ነው›› የሚለው ኢህአዴግ እንጂ፣ ከሚሠሩት ፎቆች ስር በርካታዎች ማደሪያ አልባ መኝታ ማድረጋቸውን በየቀኑ የሚታይ አሣዛኝ ገልጻ ነው፡፡ የሃገር ለውጥ የህዝብ ለውጥ ነው፡፡ ማንም ሰው ቢሆን፣ የደሞዝ ጭማሪ በሚደረግበት ጊዜ በራሱ ላይ የተወሰነ ለውጥ ይታይበታል፡፡ የሃገር ዕድገትም 11 በመቶ ከደረሰ፣ ህዝቡ በራሱ ላይ ለውጥ ሊያመጣ ይችላል ወይም አንዱ በአንዱ ላይ የሚመለከተውም ለውጥ ይኖራል ማለት ነው፡፡ በነዚህ 22 ዓመታት ግን የዚህ አይነቱን ነገር ለማየት አልተቻለም፡፡ ያ ማለት ዕድገቱ የስም ነው ማለት ነው፡፡ የፎቅ ግንባታዎች እና መንገዶች ተሰርተዋል፡፡ ያ ማለት ግን ሃገራዊ ለመፍጠር አንድ ምሣሌ ልንገራችሁ፡፡ ለልጅቱ 14 ዓመቷ ነው፡፡ የሰውነትዋ ግዝፈት ደግሞ 20 ዓመት ዕድሜ ክልል ውስጥ ያለች አስመስሏታል፡፡ አንድ ሰው ደግሞ ልጇቷን ለጋብቻ ጠየቀ፡፡ የ14 ዓመት ልጅ መሆኑዋን የሚያውቀው አባት፣ ‹‹አይ ማግባት አትችልም›› አለ፡፡ ምክንያቱም ገና 14 ዓመቷ ስለሆነ ለጋብቻ የፈለጓት ወገኖች 14 ዓመት የሚለውን ነገር ፈጽሞ ሊቀበሉ አልፈቀዱም፤ አልተዋጠላቸውምም፡፡ የልጅቱዋን የሰውነት ግዝፈት በመመልከት “ኢህአዴግ እየነገረን ያለው ዕድገትም ቢሆን የዚህ አይነት ምሳሌ ያለው ነው፡፡ እንደሚታወቀው ዛሬ ሙስና የስርዓቱ መለያ ሆኗል፡፡ በርካቶች በአንድ ጀምበር የፀሐይ ፍጥነት በሚያስደንቅ መልኩ ተቀይረው ሃብታም ሲሆኑ ይታያል፡፡ የዚህ የሃብት ምንጭ ግን አይታወቅም፤ ምክንያቱም ሥራው ሙስና ነው፡፡

አቶ በረከት

አቶ በረከት


ይህ የሙስና ተግባር ደግሞ በተለይ በአሁን ሰዓት ከፍተኛ የመንግስት ባለሥልጣናት ውስጥ ሳይቀር የገባበት ሁኔታ ታይቷል፡፡ ስርዓቱ ለይምሰል ብቻ እንደ ህዝብ ገፀ-በረከት ከዝቅተኞቻችን ተሿሚዎች መካከል ሙሰኞች እያለ ለህዝብ ቢያጋልጥም ዋናዎቹን ግን ለመንካት ታስቦ አይደለም፡፡ ይህ የሆነበት ምክንያት ደግሞ ምንም ሳይሆን አንዱ ከተነካ ሌሎችንም ይዞት የሚሄድበት የተሳሰረ የሙስና ሰንሰለት ስላለ ነው፡፡ ሌላው ነገር እንዳይነካው ሲጥር የሙስና ተግባር እየተስፋፋና አሁን አሁን ይበልጥ ወደ ሕጋዊነት እየተቀየረ የመጣበት ሁኔታ በመሰማት ላይ ይገኛል፡፡ በአንድ ሃገር ላይ ትልቁ ችግር የመንግስት ሹማምንት ሙሰኛ መሆን ነው፡፡ የሙሰኞች ቁጥር እየሰፋ በመጣ ቁጥር ተጐጂ የሚሆነውና አደጋ ላይ የሚወድቀው ማንም ሳይሆን ህዝቡ ነው፡፡ ኢህአዴግ ይህንን የሙስና ተግባር ፈጽሞ ሊያጠፋው አልቻለም፡፡ ሲታይም እንዲጠፋ የሚፈልግም አይመስልም፡፡ ባለፉት ዓመታት ‹‹የባለሥልጣናት ሃብት ምዝገባ›› በሚል አንድ ምዝገባ ተከናውኖ ነበር፡፡ ይህ ምዝገባ በቅርቡ ለህዝብ ይፋ እንደሚደረግ ቢገለጽም፣ አቶ መለስ ከመሞቱ አስቀድሞ የተደረገው ምዝገባ ለህዝብ ይፋ ሊደረግ አልተቻለም፡፡ ምክንያቱም ህዝቡ የሚያየው ሃብትና የሚገለጸው ነገር ፈጽሞ አይገናኝም፡፡ ህዝቡ የቱ ድርጅት የየትኛው ባለሥልጣን እንደሆነ አብጠርጥሮ ያውቃል፡፡ ስለዚህ የዛኔም ቢሆን ጸረ-ሙስና ኮሚሽን ከዓለም ባንክ የተቸረውን ገንዘብ ለማግኘት ሲል ይህንና ድራማ ይተውን እንጂ፣ የባለሥልጣናቱን ሃብት ለህዝብ ይፋ ያደርጋል ተብሎ ግን አይጠበቅም፡፡ ከዛ ባለፈ ደግሞ በሃገሪቱ የትምህርት ጥራትና የተማረ ኃይልን የምንመለከተው ሌላው አሳሳቢ ጉዳይ ነው፡፡ የትምህርቱ ጥራት ከመውረዱ የተነሳ ዲግሪው የከበዳቸው ወይም በ‹‹በዲግሪው›› የሚያምኑ ተማሪዎች በዝተዋል፡፡ ኢህአዴግ የትምህርት ጊዜውን ዓመት ከመቀነሱም በላይ በገፍ ተማሪዎች ያስመርቃል፣ ወደ ስር ሲገባ ግን ፈጽሞ የማይመጣጠን እየሆነ ነው፡፡ ይህ ደግሞ ትውልዱን እየገደለና እያወረደው መጥቷል፡፡ ተስፋና ለሃገርና ለወገን የሚጠቅም ተግባር የሚፈጽም ወጣት ሳይሆን፣ቀድሞተስፋ የቆረጠ ሲመረቅ ለድንጋይ ጠረባ /ኮብልስቶን/ የተዘጋጀ መሆኑን አውቆ ሃሞቱ የፈሰሰ ትውልድ ለዚህች ሃገር እያስረከበ ይገኛል፡፡
ይህ ብቻም አይደለም፡፡ በእውነቱ ከሆነ የየትኛው ባለሥልጣን ልጅ ነው በሃገር ውስጥ ወይም እነርሱ በወጣ ፖሊሲ የሚማረው? የእነርሱ ልጆቻች በአውሮፓና በአሜሪካ እያስተማሩ ሌላውን እዚህ ሃገር ውስጥ እየታሸ ለአራትና አምስት ዓመት ተምሮ ዕውቀቱን በድንጋይ ጠረባ ላይ እንዲያፈሰው እየተደረገ እንዴት የተማረ ኃይል በዚህች ሃገር ውስጥ ለራሱ ይቻላል፡፡ የህዝቡ እና የጤና ላይም ቢሆን ይበልጥ የወረደ የተለየ ለውጥ የታየበት አይደለም፡፡

eprdfኢህአዴግ ባለፉት 22 ዓመታት ቆይታው የመራው ነገር ብዙም ሚዛናዊ የሆነ ነገር አይደለም፡፡ ፖሊሲው በፈጠረው ችግር በርካቶች ከሃገር እንዲሰደዱ አድርጓል፡፡ ዛሬ በርካታዎች የሚሰደዱት የሃገሪቱ ኢኮኖሚ በመውረዱ፣ ሥራ አጥነት፣ ከዛ ባለፈ ደግሞ ፖለቲካው የሚፈጥረው ጫና ከሚፈጥርባቸው አደጋ ጋር ተያይዞ ነው፡፡ በዚህ ስርዓት የመጣ ለውጥ የለም፡፡ እስቲ ሌሎችም ጐልተው ዕድሉን በማግኘት ይሰሩ ቢባል፣ ምርጫው ግን ፈጽሞ ነፃ ሊሆን አልቻለም፡፡ “እኛ ታግለን ነው የገባነው፤ እኛ ብቻ ልንመራ ይገባል” የሚለው አካሄድ የኢህአዴግ መለያው ሆኗል፡፡ ትግል ለሕዝቦች ነፃነት እኩልነት እንጂ፣ ለአንድ ወገን ብቻ ዘላለማዊ ሥልጣን የሚሰጥ አይደለም፡፡ በፈሰሰው ደምና በተከፈለው መስዋዕትነት ሃገር ስታድግ፣ ህዝቡ ዲሞክራሲያዊ መብቱ ሲከበር ደስ ይላል፡፡ ይሄ ግን ኢህአዴግ ጋ አይሰራም፡፡ ቢቻል ዘላለማዊ አገዛዝን በመያዝ ወይም ‹‹ልንመራ የሚገባን እኛ ነን›› የሚል ፖሊስ ይዟል፡፡ ይህ ደግሞ ሊሆን የሚችል አይደለም፡፡ ዛሬ ዓለም ተቀይሯል፤ ምናልባት ኢትዮጵያን ጨምሮ ውስን የአፍሪካ ሃገራት ላይ የአንድ ፓርቲና ወገን በበላይነት ሰፍኖ ሊታይ ይቻላል፡፡ ከዛ ባለው ግን ዲሞክራሲያዊ ምርጫ ለማድረግ የሥልጣን ሽግግር እያየን ነው፡፡ አቶ በረከት ባለፈው ሰሞን የነገሩን “የዘፈንዳር ዳሩ ነው” እንደሚለው፣ ተረት አሁንም በሥልጣን ላይ ለመቆየት እንደሚፈልጉና ይህንን ለማድረግ ደግሞ የተጀመሩትን የልማት ሥራዎች ‹‹በቀብድነት›› በማስገባት እንደው ነገሩን ለማስመሰል ጥረዋል፡፡ ኢህአዴግ ይህን አያደርግም አይባልም፡፡ ባቀጣይነት የሃገሪቱ ውድቀት እንደሚቀጥል መዘንጋት የለበትም፡፡

የአዉሮፓ ሕብረት የሚሊዮኖች ድምጽ ንቅናቄን በተመለከተ አንድነትን አነጋገረ

$
0
0

(ፍኖተ ነፃነት) በኢትዮጵያ የአዉሮፓ ሕብረት ልኡካን ቡድን መሪ አምባሳደር ቻንታል ሔበሬሽ፣ በአዉሮፓ ሕብረት የአፍሪካ ቀንድ እና የሕንድ ዉቂያኖስ አካባቢ ዴስክ ኦፌሴር ቪክቶሪያ ጋርሲያ ጉሌን እንዲሁም ቶማስ ሁይገባርቴስ የተሰኙ ፣ የአዉሮፓ ሕብረት ሃላፊ ፣ በነርሱ አነሳሽነት፣ ከአንድነት ፓርቲ ከፍተኛ አመራር አባላት ጋር ሰፊ ዉይይት አደረጉ።
bahar dar 14
ከአንድ ሳምንት በፊት በኢትዮጵያ ስላለው የዲሞክራሲ ግንባታ ዙሪያ ከጠ/ሚኒስተር ኃይለማሪያም ደሳለኝ ጋር እንደተነጋገሩ የገለጹት የአዉሮፓ ሕብረት ባለስልጣናት፣ የአንድነት ፓርቲ በጠራዉ የሚሊዮኖች ድምጽ ሁለተኛ ዙር ንቅናቄ እንዳሳሰባቸው በመገለጽ፣ አንድነት በሚያደርጋቸው እንቅስቃሴዎች ዙሪያ፣ ፓርቲው ፍቃደኛ ከሆነ ማብራሪያ እንዲሰጣቸው፣ ጠይቀዋል።

የአንድነት ፓርቲ ወክለው ከአዉሮፓ ሕብረት ጋር የተነጋገሩት ሊቀመንበሩ ኢንጂነር ግዛቸው ሽፈራዉና የሕዝብ ግንኙነት ክፍል ሃላፊው አቶ ሃብታሙ አያሌው በበኩላቸው ያሉትን ሁኔታዎች ለማስረዳት ሞክረዋል።

አንድነት አሁን የሚያደርገው የሚሊዮነሞች ንቅናቄ ከዚህ በፊት ከተደረገው የቀጠለ እንደሆነ ያስረዱት የአንድነት አመራር ፣ ፓርቲዉ አዲስ አበባ ጨምሮ በ17 ከተሞች ፣ በፍትህ እና በላንድ ሪፎርም ዙሪያ ፣ ከሕዝብ ጋር ዉይይቶችን እንዲሁም ሰላማዊ ስለፎች እንደሚያደርግ ገልጸዋል። አንድነት ከዚህ በፊት ባደረጋቸዉ በርካታ ሰልፎች አንዳች አይነት በሰውም ሆነ በንብረት ላይ የደረሰ ጉዳት እንደሌለ የገለጹት የአንድነት አመራር አባላት ፣ ወደፊት የሚደረጉ እንቅስቃሴዎች፣ ሰላማዊና ሕዝባዊ እንደሚሆኑ በማስረዳት ፣ አንድነት አገር አቀፍ መዋቅሩን እያሰፋ እንደሆነም ለማሳየት ሞክረዋል።

Habitamu Ayalewየአዉሮፓ ሕብረት ተወካዮች፣ አንድነት ይዞት የተነሳዉ የመሬት ጥያቄ ተገቢና ወቃታዊ፣ ለኢትዮጵያ ጥቅም የሚያመጣ እንደሆነ የገለጹ ሲሆን፣ በመጪው የ2010 ምርጫ ዙሪያ አንድነት ያለውን አቋም እንዲያስረዳቸው ጠይቀዋል። «ለምርጫ አስፈላጊውን ዝግጅት እያደረገን ነው። በሁሉም ክልሎች ለፌዴራልም ሆነ ለክልል ተወዳዳሪዎች ከወዲሁ እያዘጋጀን ነው» ሲሉ የመለሱት የአንድነት አመራሮች ፣ በምርጫ መሳተፉና አለመሳተፉ ግን ወደፊት የሚወሰን እንደሆነ ገልጸዋል። «ኢሕአዴግ ሁሉንም ነገር ከዘጋዉና የፖለቲካ ምህዳሩን ካጠበበው. የምርጫ ቦርድ የመሳሰሉ ተቋማት ገለልተኝነት ከሌላቸው፣ ምርጫ መሳተፉ ዋጋ እንደማይኖረዉ የገለጹት የአንድነት አመራራ፣ በምርጫዉ ጉዳይ፣ ኳሷ ኢሕአዴግ ሜዳ ላይ እንዳለች አስረድተዋል።

የፖለቲካ እስረኞችን ሁኔታ የጠየቁት የአዉሮፓ ሕብረት ተወካዮች «እስረኞችን ለመጠየቅ ይፈቅድላቹሃል ወይ ? » ተብለው ለተጠየቁት ጥያቄ፣ አንዱዋለም አራጌን አንድ ጊዜ ለመጠየቅ እንደቻሉ ነገር ግን ርዮት አለሙን፣ እስክንደር ነጋ እና ናትናኤል ሞኮንን እንዳይጠይቁ መከልከላቸውን የአንድነት አመራሮች አስረድተዋል።

በፊታችን ኤፕሪል በብራሰልስ፣ በአዉሮፓ ሕብረት እና በአፍሪካ ሕብረት መካከል ስብስባ እንደሚደረግ የገለጹት የአዉሮፓ ሕብረት ተወካዮች፣ የአንድነት ፓርቲ በስብሰባው እንዲገኝ ጥሪ ያቀረቡ ሲሆን፣ በገዠዉ ፓርቲ ዘንድ የፊታችን ምርጫ ፍትሃዊና ዴሞክራሲያዊ እንደሚሆን ቃል እንደተገባላቸው ተናግረዋል።

የአንድነት አመራሮች ግን ገዢዉ ፓርቲ የሚናገራቸውና ተግባራቶቹ አንድ እንዳልሆኑ፣ ይሄ ነው የሚባል፣ የዲሞክራሲ ግንባታዉን የሚያግዝ የተጨበጠ እርማጃ እንዳልወሰደ መረጃ ላይ በመደገፍ ገለጻ አድርገዉላቸዋል። «ጋዜጦቻችንን ማተም አልቻልም። ደጋፊዎቻችን ይታሰራሉ። ከሥራ ይባረራሉ። ሰልፍና ስብሰባዎች ስንጠራ ብዙ ጊዜ እንግልት ይደርስብናል» ሲሉም በአገዛዙ እየተፈጸሙ ያሉ ከፍተኛ የሰባአዊ መብት ጥሰቶችን ዘርዝረዋል።

በዉጭ አገር ስላሉ ኢትዮጵያዉያንም የአንድነት ፓርቲ አመራሮች ለቀረበላቸው ጥያቄ ምላሽ ሰጥተዋል። «በዉጭ ያለው ኢትዮጵያዊ ወደ 2 ሚሊዮን ይጠጋል። በርካታ ደጋፊዎች አሉን። በተለያዩ ቦታዎች በተለይም በአሜሪካ የድጋፍ ድርጅቶች አሉን» ያሉት የአመራሩ አባላቱ፣ የድጋፍ ድርጅት ዉስጥ የሌሉ፡ ነገር ግን የምናደርጋቸውን ከፓርቲ በላይ የሆነውን የሚሊየኖች ንቅናቄን የሚደገፉ በርካታ ኢትዮጵያዊ የሲቪክ እና የፖለቲካ ድርጅቶች እንዳሉም አስረድተዋል። የትግሉ አካል ከሆኑና በዉጭ ካሉ ኢትዮጵያዉያን ጋር ለመነጋገር፣ አንድነት የልኩካን ቡድኖች በቅርቡ ወደ ዉጭ እንደሚያስማራም ለአዉሮፓ ሕብረት ተወካዮች ገልጸዋል።

በአገሪቷ ያሉትን ችግሮች ለመፍታት እንዲቻል የተሻለዉና የሰለጠነው አማራጭ፣ መነጋገር እንደሆነ ያስረዱት የአንድነት አመራር አባላት፣ አንድነት ከኢሕአዴግ ጋር ሆነ ሽብርተኞች ተብለው ካልተሰየሙ ደርጅቶች ጋር ሁሉ ያለ ምንም ቅድመ ሁኔታ ለመነጋገር ፍቃደኛ እንደሆነ፣ ለዚያም ጥሪ እንዳቀረቡ ገልጸው፣ አገዛዙ ግን ቅድመ ሁኔታዎች እያስቀጠ በተደጋጋሚ ለመነጋገር ፍቃድኛ እንዳለሆነ ተናግረዋል።

Sport: የማን.ዩናይትዱ ዳረን ፍሌቸርና በአንጀት ህመም በተያዘበት ወቅት ያሳለፈው ስቃይ

$
0
0

በማንችስተር ዩናይትድ ካሪንግተን የልምምድ ማዕከል በአንዱ አነስተኛ የስብሰባ አዳራሽ አንድ ዝግጅት ተስተናግዶ ነበር፡፡ አሰልጣኝ ዴቪድ ሞዬስ ቡድናቸውን በሚገነቡበት ማዕከል ስብሰባው ይደረግ እንጂ ከዩናይትድ አስቸጋሪ የውድድር ዘመን ጋር የሚያገናኘው ነገር አልነበረም፡፡ አስቸጋሪ በሽታን ለመዋጋት የተዘጋጀ የእርዳታ ማሰባሰቢያ ራት ግብዣ እንጂ፡፡
Darren-Fletcher_2644581
ዳረን ፍሌቸር የግብዣው አንዱ ባለጉዳይ ነው፡፡ ‹‹Collitis›› በተሰኘው የአንጀት ህመም ሲሰቃይ ቆይቶ በቅርቡ በሙሉ ጤንነት ወደ ጨዋታ የተመለሰው የማንችስተር ዩናይትድ አማካይ ብቸኛው የህመሙ ሰለባ አይደለም፡፡ የቀድሞው የእንግሊዝ ራግቢ ብሔራዊ ቡድኑ ተጫዋች ሉዊስ ሙዲም እንዲሁ በከባዱ ህመም አልፏል፡፡ ባለፈው ምሽት የተዘጋጀው ግብዣም በሁለቱ ሰዎች አስተባባሪነት የህመሙን ሰለባዎች ለመረዳት ምግባረ ሰናይ አላማ ያነገበ ነው፡፡

በግብዣው ላይ ፍሌቸር ከዚህ ቀደም ስቃዩን ከገለፀበት የበለጠ የችግሩን አስከፊነት ዘርዝሯል፡፡ ለረጅም ጊዜ አብሮት የቆየው ህመም የእግርኳስ ተጨዋችነት ህይወቱን ከፍፃሜ ሊያደርሰው ተቃርቦ እንደነበር ከዚህ በፊትም መግለፁ ይታወሳል፡፡ አሁንም ህመሙን እያስታወሰ ሲናገር ሳግ ይተናነቀዋል፡፡ ድምፁ ቁርጥ ቁርጥ ይላል፡፡ ህመሙን ውጦ በቡድን ጓደኞቹ ፊት ጤናማ መስሎ ለመታየት ሞክሯል፡፡ ደዌው እንደጀማመረው በነበሩት የመጀመሪያ ወራት ከሰር አሌክስ ፈርጉሰን በስተቀር ለተቀሩት የቡድኑ አባላት በምስጢር ይዞት ነበር፡፡

‹‹ከልምምድ የምቀርበትን ምክንያት ለማወቅ ሲጠይቁኝ እዋሻለሁ፡፡ የፈጠራ ሰበቦችን ማዘጋጀት ነበረብኝ፡፡ በልምምድ ላይ ስገኝ መታመሜ ይታወቃል፡፡ ህመሜን ለመናገር ግን አልፈልግኩም፡፡ ወደ መፀዳጃ ቤት የምመላለስበትንም ምክንያት እንዲሁ የራሴ ምስጢር ነበር፡፡

‹‹ፕሮፌሽናል እግርኳስ ተጫዋች ነኝ፡፡ በፕሪሚየር ሊግ እና በማንችስተር ዩናይትድ እጫወታለሁ፡፡ በቃ! እዚህ ደረጃ በመገኘቴ ከዓለም አናት ላይ የወጣሁ ይመስለኝ ነበር›› በማለት በህመሙ ብዙ መማሩን ፍሌቸር ያምናል፡፡ በፍሌቸርና በሙዲ እንደተተረከው ህመሙ ጨካኝና እጅግ አስቸጋሪ ነው፡፡ አንጀት እንዲጉረበረብ ያደርጋል፡፡ ድውያን አሁንም አሁንም ወደ መፀዳጃ ቤት ለመመላለስ ይገደዳሉ፡፡ ‹‹በቀን ከ10 እስከ 30 ጊዜ ድረስ መፀዳጃ ቤት መግባት ግድ ያልል፡፡ በዚህ ሂደት ላይ ብዙ ደም ከሰውነትህ ይወገዳል›› ይላል የ30 ዓመቱ ስኮትላንዳዊ፡፡

ፍሌቸርና ሙዲ ‹‹United fore Colitis›› የተሰኘውን የራት ፕሮግራም ያዘጋጁት በዩናይትድ ኪንግደም ለሚገኘው የኮሊቲስ ማህበር የገንዘብ ድጋፍ ለማሰባሰብ ነው፡፡ በመጪው ወር በኦልድ ትራፎርድም ተመሳሳይ የእርዳታ ዝግጅት ይኖራል፡፡

ፍሌቸር ከህመሙ እስኪፈወስ ድረስ በቅርብ ርቀት መፀዳጃ ቤት ወደሌለበት ቦታ አይጓዝም ነበር፡፡ ልጆቹን እንኳን ወደ መናፈሻ ወይም ስታዲም መውሰድ በማይችልበት ደረጃ ተፈትኗል፡፡ የራግቢው ተጨዋች ሙዲም በሽታውን ለሁለት ዓመታት ያህል ከቡድን ጓደኞቹ ደብቋል፡፡ ከራግቢው ክለብ የልምምድ ማዕከል 40 ደቂቃ ጉዞ ርቀት ላይ ይኖር ነበር፡፡ ከመኖሪያ ቤቱ ወደ ማዕከሉ ለመሄድ ሲያስብ ግን ስለ ጉዞው በጥልቀት ማሰብ ግድ ነበር፡፡ ‹‹ለዚያን ያህል ጊዜ በመኪና ውስጥ መቆየት በኮሊቲስ አልሰር ለተጠቃ ህመምተኛ ሰው የሚቻል አይደለም፡፡ በ40 ደቂቃው ጉዞ መካከል ለ10 ወይም 11 ጊዜ መኪናውን እያቆመ መፀዳጃ ቤት መፈለግ ግድ ይለዋልና›› ይላል፡፡

ያን ጊዜ ሙዲ ሌይስተር ታይገርስ ለተባለው የራግቢ ክለብ ይጫወት ነበር፡፡ እዚያ ለመድረስ የአምስት ደቂቃ ጉዞ ብቻ ያስፈልጋል፡፡ ሆኖም በጉዞው ላይ ከሶስት እስከ አራት ጊዜ የመቆም ግዴታ ነበረበት፡፡ በችግሩ ምክንያት ለልምምድ ማዕከሉ በጣም የሚቀርብ መኖሪያ ቤት አግኝቶ መኖር ጀመረ፡፡ ‹‹አንዳንድ ጊዜ መፀዳጃ ቤቱ አምስትና ስድስት ሜትር ቅርብ ሆኖ ሳለ ሩቅ ይሆናል›› ሙዲ ያክላል፡፡

ፍሌቸር ግን ምስጢሩን ደብቆ መዝለቅ ተሳነው፡፡ ቁርጡ ቀን ሲመጣ ለቡድን ጓደኞቹ ችግሩን ነገራቸው፡፡ ‹‹ለካ ልትሞት ደርሰሃል›› ሲሉ በግምት አደመጡት፡፡ ህክምናውን እንዲከታተል መከሩት፡፡ (ምክራቸው) አበረታች ነበር›› ይላል ወቅቱን ሲያስታውስ፡፡ የፍሌቸር ህመም በይፋ ከታወቀ በኋላ መልዕክቱን ከፃፉት መካከል በተመሳሳይ ህመም በተጠቁ ልጆቻቸው ጤና ግራ የተጋቡ ወላጆች ይበዙበታል፡፡ በእንግሊዝ በበሽታው ብዙሃን ህፃናት ይጠቃሉ፡፡ በየዓመቱ በ10 ሺዎች የሚቆጠሩ ዕድሜያቸው ከ25 ዓመት በታች የሆኑ ህፃናት በበሽታው ይያዛሉ፡፡ ወላጆች በልጆቻቸው ላይ ስለደረሰው ለተጨዋቹ ያዋዩታል፡፡ በትምህርት ቤት በኮሊቲስ ህመም ተይዣለሁ ከማለት ይልቅ እንደ ፍሌቸር ታምሜያለሁ ማለትን እንደሚችሉ ገልፀውለታል፡፡

የፍሌቸር ጉዞ ምን ያህል የማይመች እንደነበር ድብቅ አይደለም፡፡ በተለይ ህመሙ በድጋሚ በተመለሰበት በ2010 ዙሪው ጨለመበት፡፡ ለፈውስ ለመብቃት ሶስት አይነት ቀዶ ጥገና አስፈለገ፡፡ ‹‹በተደጋጋሚ ባደረግኩት የደም ምርመራ ህመሙ ከፍተኛ ደረጃ ላይ የመድረሱን ውጤት አወቅኩኝ፡፡ እናም ለሁለት ጊዜ ያህል ጉልኮስ ተሰክቶልኝ በሆስፒታል ለመተኛት ተገደድኩ፡፡ ምክንያቱም በጣም አድክሞኝ ነበርና ነው፡፡

‹‹በጣም ፈርቼ ነበር›› ፍሌቸር ይቀጥላል፡፡ የህመሙን ሁኔታ አስመልክቶ ከዶክተሮች ቁርጡን ለመስማት እንኳን አራት ሳምንታት ፈጁበት፡፡ በኋላም በ2012 ለስድስት ወራት ከእግር ኳስ መራቅ አስፈለገው፡፡ ሰዎች እየመጡ ሀሳባቸውን ይሰጡታል፡፡ ‹‹የእግርኳስ አካላዊ ባህሪይ ለህመም ዳርጎሃል›› አሉት፡፡ ከዩናይትድ ርቆ ጤንነቱ ላይ አተኮረ፡፡ ልምምዱን ትቶ ጤናው አልተመለሰለትም፡፡ ህመሙ ቀጠለ፡፡ ልምምዱን ትቶ ጤናው አልተመለሰለትም፡፡ ህመሙ ቀጠለ፡፡ ልምምዱን ሰርቶም፣ ሳይሰራም መታሙ ግን የችግሩ መንስኤ እግርኳስ እንዳልሆነ ማረጋገጫ ሆነለት፡፡ በዚህም ተደሰተ፡፡ ‹‹እግርኳስን ስለምወደውና ከቶም መጫወትን ማቆም ስለማልፈልግ ህመሙ መቀጠሉ አስፈላጊ ነበር፡፡ እግርኳስ ለህመሜ ምክንያት አይደለም፡፡ ለስቃይ የተዳረግኩት በህመሙ እንጂ በእግርኳስ አልነበረም፡፡
ሁለቱም ስፖርተኞች በህመሙ ምክንያት ጫማቸውን ሊሰቅሉ አልተገደዱም፡፡ ‹‹ከአካላዊ ህመሙ ይልቅ ስነ ልቦናዊ ጉዳቱ ያይላል›› ይላል ፍሌቸር፡፡

አሁን ጨለማው አልፏል፡፡ ፍሌቸርም ሙሉ ለሙሉ ተፈውሷል፡፡ በቻምፒዮንስ ሊግ የጥሎ ማለፍ ዙር ስኳድ ዝርዝር ውስጥም ተመዝግቧል፡፡ ማንቸስተር ዩናይትድ ከአስቶንቪላ ጋር ባደረገው ጨዋታ ወደ ሜዳ ሲመለስ ከተጫዋቾች አስደናቂ አቀባበል ተደረገለትት፡ ከጨዋታው በኋላም በመልበሻ ቤት የቡድን ጓደኞቹ በዝማሬና በጭብጨባ በጤና መመለሱን አበሰሩለት፡፡ ከስቶክ ሲቲ ጋር ሲወቱም ደጋፊዎች ‹‹ፍሌቸር ጎል ካስቆጠረ ወደ ሜዳ እንገባለን›› እያሉ አዜሙለትት፡

ሶስቱ ቀዶ ህክምናዎች ህመሙ እንዳያገረሽ ዋስትና እንደሚሆኑ ተጫዋቹ ይናገራል፡፡ በዚያች ሀገር ለሚኖሩት ፍሌቸር ተስፋ ነው፡፡ በራት ግብዣው ላይ ከተገኙት እንግዶች አንዱ ሰር አሌክስ ፈርጉሰን ናቸው፡፡ በዝምታ አልተደመሙም፡፡ የበኩላቸውን ሀሳብ እንዲህ ሲሉ ሰንዝረዋል፡፡ ‹‹የቡድን ጓደኞቹ ለማያውቁት ችግር ድጋፍ ሲያደርጉ መመልከት ለእኔ ትርጉሙ ብዙ ነው››

Health: በዱካክ ተሰቃየሁኝ፤ ምን መፍትሄ አላችሁ? – (የሃኪሙን ምላሽ ይዘናል)

$
0
0

ዕድሜዬ 17 ዓመት ሲሆን በ10+3 ፕሮግራም የኮሌጅ ትምህርቴን ከጀመርኩ ወራትን አስቆጥሬያለሁ፡፡ ከዚህ በላይ ግን በትምህርቴ መግፋት የምችል አይመስለኝም፡፡ የደረሰብኝ ችግር ትምህርቴን ማስተጓጎል ብቻ ሳይሆን አጠቃላዩ ኑሮዬንም ምስቅልቅሉን እያወጣው ነው፡፡

እንደሚታወቀው ክላስ ገብቼ ትምህርት መማር የምችለው ቀን ቀን ነው፡፡ ከአንድ ወር ገደማ በፊት ይመስለኛል ክፍል ውስጥ እንቅልፍ እየወሰደኝ ተቸግሬያለሁ፡፡ ከአየሩ መቃትነት የተነሳ ደግሞ ታግዬ እንኳን የምቆጣጠረው አልሆነልኝም፡፡ ይህ ችግሬ በአሁኑ ጊዜ በጣም እያሳፈረኝ ነው፡፡ ችግሬን እንደ ችግር ቆጥሮ የሚያዝንልኝ ሰው እንኳን የለም፡፡ በስርዓት ተቀምጬ አስተማሪ በምከታተልበት ሳላስበው ዥው ያለ እንቅልፍ ይወስደኛል፡፡ ግንባሬን ከዴስኩ ጋር የማጋጭበት ጊዜም ብዙ ነው፡፡

ይህን ችግሬን ያወቁ ልጆች ወደ ኋላ አካባቢ እንድቀመጥ መከሩኝና ያሉትን አደረግሁ፡፡ እኔ ስተኛ ግን ክላሱ እስኪያልቅ ድረስ የሚቀሰቅሰኝ ሰው የለም፡፡ ይህስ ባልከፋ፣ ሆኖም ወዲያው እንቅልፍ እንደወሰደኝ የሚያሳቅቅ ነገር ይደርስብኛል፡፡ ምን መሰላችሁ ይሄ እንደ ዱካክ ነገር ደረቴን ፈጥርቆ ይዞ እንዳልንቀሳቀስ ያሳስረኝና ሳላስበው ቀጭን ጩኸት አሰማለሁ፡፡ በዚህ ጊዜ ነው መምህሩ መተኛቴን የሚያውቁት፡፡ ተቀስቅሼ ስነቃ ደግሞ ተማሪው ሁሉ እየሳቀብኝ ነው፡፡ ታዲያ በዚህ ሁኔታ እንዴት አድርጌ ነው የምማረው? ይኸው ትምህርት ካቋረጥኩ ሁለት ሳምንት ሆኖኛል፡፡
ይህ ዱካክ እና በቀን የመተኛት አባዜ መፍትሄ አለው ትላላችሁ? ማብራሪያችሁን በጉጉት እጠብቃለሁ፡፡
የእናንተው ጢኖ

የዶ/ር ዓብይ ዓይናለም ምላሽ፡- ውድ ጢኖ ለጥያቄህ ልባዊ ምስጋና ለማቅረብ እንወዳለን፡፡ ሳይታሰብ እና ሳፈለግ የሚመጣ የቀን እንቅልፍ በአጠቃላይ ህይወት ላይ የሚያመጣው ምስቅልቅ እጅግ በጣም ከባድ በመሆኑ ቅድሚያ ሰጥተነዋል፡፡
ምናልባት ለትምህርትህ ከምትሰጠው ላቅ ያለ ግምት አንፃር ክፍል ውስጥ ተቀምጠህ የማንቀላፋቱን ነገር የበለጠ ትኩረት ሰጠኸው እንጂ ህመሙስ ከዚህ የባሰም ፈተና ሊያስከትልብህ ይችላል፡፡ ሳይፈልጉ በቀን መተኛት በጣም መጥፎ ክስተት ነው፡፡ ህመሙ በህክምናው ዓለም ‹‹Narcolepsy›› ተብሎ ይጠራል፡፡

‹‹Narcolepsy›› የእንቅልፍ መዛባት ቢሆንም ከሌሎች ተያያዥነት ካላቸው የእንቅልፍ መዛባት ችግርህ ለየት የሚያደርገው ቁጥራቸው በጣም ውስን በሆኑ ሰዎች ላይ የሚከሰት ህመም በመሆኑ ሳቢያ ነው፡፡ አልጋ ላይ ተጋድመው አይናቸውን ቢጨፍኑም እስከ ውድቅት ሌሊት ወይም እስከ ንጋት ድረስ እንቅልፍ አልወስድ ብሏቸው ሲገላበጡ የሚያድሩ ብዙዎች ናቸው፡፡ እንቅልፍ ሸለብ ሲያደርጋቸውም ግማሽ ሰዓት ወይም አንድ ሁለት ሰዓት ብቻ ከቆዩ በኋላ ተመልሰው የሚነቁና የቀረውን የሌሊት ክፍል ፈጠው የሚያድሩም ጥቂት አይደሉም፡፡ ሌሎቹ ደግሞ ጠዋት ከእንቅልፋቸው መንቃት ተስኗቸው ተጋድመው ያረፍዳሉ፡፡ ከዚህ አንፃር ‹‹Narcolepsy›› የጥቂቶች ብቻ ችግር ነው፡፡
sleep disorder
‹‹Narcolepsy›› በጣም አደገኛ ህመም ነው፡፡ የዕለት ስራን በወጉ ለማከናወን፣ ለመብላት፣ ለመዝናናት፣ ወዲያ ወዲህ ብሎ ለመንቀሳቀስ የህሊና ንቃት ያስፈልጋል፡፡ በተለይም የመኪና መንገድ ለማቋረጥ፣ ማሽን ላይ ለመስራት ወይም መኪና ለማሽከርከር ብሩህ የአዕምሮ ንቃት ማስፈለጉ የግድ ይላል፡፡

በእርግጥ ይህ ህመም ያለባቸው ሰዎች ተረጋግተው ክፍል ውስጥ መማር ይከብዳቸዋል፡፡ ከዚህ ህመም ጋር በተያያዘ መልኩ የሚከሰት አንድ ሌላ ችግር አለ፤ ይህም በተለምዶ ‹‹ዱካክ›› እየተባለ የሚጠራውና በእንቅልፍ ዓለም ውስጥ ሆነው መሰቃየት ሲሆን በጣም የሚያስጨንቅ ጉዳይ ነው፡፡
ይህ ሁኔታ ‹‹Sleep paralysis›› ተብሎ ይጠራል፤ ዱካክ እንደማለት ነው፡፡ በእርግጥ ከቀን እንቅልፍ ‹‹Narcolepsy›› ጋር ባልተያያዘ ሁኔታም ሊከሰት ይችላል፡፡ በተለይም ታዳጊ ህፃናት እና ጎረምሶች ናቸው በዚህ ችግር የሚጠቁት፡፡

ህመሙ ህክምና ያስፈልገዋል፡፡ አለበለዚያ ግን በሽተኛውን ለአደጋ ወይም ለሞት የሚዳርግ ክስተት ያስከትልበታል፡፡

ውድ ጠያቂያችን የስነ አዕምሮ ሐኪሞች ክትትል የግዴታ ያስፈልጋል፡፡ የሚታዘዙልህ መድሃኒቶች ጥንቃቄ ካልታከለባቸው በጣም አደገኞች በመሆናቸውም ሁኔታህ እየታየ የመድሃኒቶቹ መጠን ያስተካክልም ዘንድ መጠቆም እንወዳለን፡፡

ኃይለማርያም ደሳለኝ በዳንስ ላይ (ዜና ፎቶ)

Viewing all 15006 articles
Browse latest View live