Quantcast
Channel: Ethiopian News | ዘ-ሐበሻ | Latest News Provider | News For All
Viewing all 15006 articles
Browse latest View live

ሕወሀትና የኢትዮጵያዊነት ገጽታው

$
0
0

በናትናኤል ካብቲመር (ኦስሎ ኖርዌይ)

(ናትናኤል ካፕትይመር)

(ናትናኤል ካፕትይመር)

ባለፈው የካቲት 11 2006 የህወሃት ምስረታ በአል ሲከበር ጠ/ሚንስትር ሀይለማርያም ደሳለኝ ያደረጉትን ንግግር ሲጀምሩ የትግራይ ሀዝብ ከአስከፊው ብሄራዊ ጭቆናና ፋሽስታዊ ስርአት ጋር ተናንቀው ……. ብለው ነበር እናም በርግጥ የህወሀት የትግል መስመር እና አለማ ምን ነበር? አሁን እንደሚባለው ኢትዮጵያን ከአስከፊው የደርግ ስርዐት ለመታደግ ወይስ በአንድ ወቅት መለስ ዜናዊ እነደተናገሩት “የድህነት ጠበቃ የነበረውን ደርግ” አሸንፎ ብልጽግና ለማምጣት?

ሕወሐት የተመሰረተበትን አላማ የሚገልጽ የህወሀት ማኒፌስቶ (በ 1968 የታተመ መጸሔት) ለዚህ ጥሩ መልስ አለው ሰነዱ ላይ በግልጽ እንደተቀመጠው አጠቃላይ የህወሀት አላማ እና መድረሻ “የጨቋኟ አማራ ብኄርን” ጭቆና ለማስወገድ እና የትግራይ ሪፓብሊክ ማቋቋም ነው፡፡ ስለኢትዮጵያ እድገትም ሆነ የወደፊት አላማ ያስቀመጠው የልማት እቅድ ሳይሆን የኢትየጵያን አንድነት በሚያፈራርሱ ዘረኛ አስተሳሰብ የታጨቀ ነው፡፡ ለዚህም ይመሰላል ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር የሚለውን ዘወትር በሸገር ራዲዮ የምንሰማውንና ሁሉም ኢትዮጵያዊ የሚወደውን አባባል የጎሪጥ የሚመለከቱት ብዙ የነበሩት፡፡ ስለዚህም የህዝቡን ስሜት ከዚህ ለማስለወጥ ብዙ ነገሮቸ ተብለዋል፡፡ ለምሳሌ የዚሁ ስርአት አጫፋሪ በሆነው ኢትዮ ቻናል በተባለው ጋዜጣ ላይ (እትሙን አላስታውሰውም) ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር የሚለውን ክቡር ቃል አጅግ ተራ በሆነ አቀራረብ ምንም ነገር ለዘላለም አይኖርም ስለዚህ ይህ አባባል ስህተት ነው የሚል ትርጉም ሰጥቶ አፍራሽ ፕሮፓጋንዳውን ይዞ ብቅ ያለው፡፡ በነራችን ላይ ዘላለማዊ ክብር ለሰማዕታት የሚሉንም እነሱው ናቸው አናም ዘላለም የሚለው ቃል ትርጉም ሳይገባቸው ቀርቶ ሳይሆን ጠባቸው ከኢትዮጵያዊነት ጋር ስለሆነ ነው ፡፡
አሁን ጠዋት ማታ የሚያደነቁረን የኢህአዴግ ፕሮፓጋንዳ የሚነግረን የኢትዮጵያ አንድነት የሚረጋገጠው ኢህአዴግ ያመጣው የዘር ፖለቲካ በነሱ አገላላጽ “የብሄር ብሄረሰቦች እኩልነት ሲረጋጋጥ” መሆኑን ነው፡፡ የብሄር ብሄረሰቦች እኩልነት ተረጋግጧል በሚሉት በዚህ ዘመን የትግራይ ተወላጅ (የህወሃት አባል) መሆን ብቻ ሁሉም በሮች እንዲከፈቱለት የሚያደርግ ልዩ የይለፍ ካርድ መሆኑን የምናየው የአደባባይ ሚስጥር ነው፡፡ እዚህ ላይ ሁል ጊዜ የሚያስገርመኝን አንድ ማሳያ ላስቀምጥ፤ ብዙ የትግርኛ ተናጋሪ ያልሆኑ ሰዎች (በተለይም የስርአቱ አጫፋሪዎች)ንግግር ሲኖር ወይም ትንሽ ጭቅጭቅ ሲኖር ልክ የትግራይ ተወላጆች እነደሚሉት ዋእ! ዋእ! ሲሉ እንሰማለን፡፡ ዘወትር ፈገግ ቢያሰኘኝም ለኔ የዚህ ትርጉሙ ብዙ ነው በጣም ብዙ።፡፡
tplf
እንደምናስታውሰው ኢህአዴግ ስልጣን ከያዘበት ጀምሮ ስለ ኢትዮጵያ አንድነት ስለ ሀገር ፍቅር የሚናገሩ ነገሮች በሙሉ በመንግስት ሚዲያዎች በአዋጅ የተከለከሉ ይመስል አስከ ቅርብ አመታት ድረስ መስማት ብርቅ ነበር፡፡ በተለያዩ አጋጣሚዎች ኢትዮጵያዊነትን ከህዝቡ አእምሮ ለመነጠል በስውር አንዳንዴም በግልጽ የሚደረጉ ግፊቶች ነበሩ፡፡ አሁንም በተለይ ለዚህ ዘመን ትውልዶች ሀገራችን የረጀም ግዜ አኩሪ ታሪከ እንዳላት ሳይሆን ተራ የሆነ የዘር ፖለቲካ እንደ አኩሪ ታሪክ ይማራሉ፡፡ የሃገራችን ህፃናት ማንነታቸውን ረስተው የፈረንጅ ቋንቋ የሚናገሩ ሆነው እየተቀረጹ ነው፡፡ በሃገራቸው ቋንቋ አንድ ዓረፍተ ነገር ተናግሮ መጨረስ ሲተናነቃቸው እያስተዋልን ነው። አንድ ሰው 12 አመት መሉ ተምሮ እንግሊዝኛ መናገር የዕውቀት ጣሪያ እስኪመስል ድረስ ዛሬ በሀገራችን በተለይም በአዲስ አበባ የልጆች የአፍ መፍቻ ቋንቋ እንግሊዝኛ መሆን ከጀመረ ቆይቷል፡፡ በሌላ መልኩ ደግሞ በክልሎች አካባቢ በአፍ መፍቻ ቋንቋ ትምህረተ ከመሰጠቱ ጋር ተያይዞ (በነገራችን ላይ በአፍ መፍቻ ቋንቋ መማር በራሱ ችግር የለውም) እነዚህ ተማሪዎች ሌሎች ቋንቋዎችን በተለይም አማርኛን እንዲጠሉ በመደረጋቸው የሀገራቸውን ብሄራዊ ቋንቋ መናገር የማይችሉ ዜጎች ማየት ጀምረናል፡፡

ሀገራችን ኢትዮጰያ አንድነቷ ተከብሮ የኖረው በልጆቸዋ ውድ መስዋትነተ እንደሆነ ማወቅ ማንነትን ማወቅ እንጂ የብሄር ጭቆና ማስታወስ አይደለም በነገራችን ላይ ኢትዮጵየዊነትን ከአማራ ብሄርተኝነት ጋር ማገናኘት አንዱ የህወሃት አስገራሚ የውሸት ፕሮፓጋንዳ ነው፡፡ ሁሉም ማወቅ ያለበት ግን ህወሃትም ሆነ እርሱ የሚመራው ኢህአዴግ ከምስረታው ጀምሮ ኢትዮጰያዊያንን በዘር ከመከፋፈል ውጭ ሰለሀራችን ኢትዮጵያና ህዝቦችዋ ሁለንተናዊ አድገት የማይጨነቅ መሆኑን ነው፡፡ስለዚህ እኛ ኢትዮጰያዊያን ፀረ ኢትዮጰያ አቋም ያለውን አስከፊ ስርዐት ማስወገድና ልጆቻችንን ታላቅ ሀገር እንዳላቸው ማስተማር ለነገ ብለን የማናሳድረው ሀላፊነት ይመስለኛል፡፡

ኢትዮጲዊነት ያሸንፋል!! ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር!!
natnaelkab@gmail.com

↧

↧

የአድዋ ድል እና የአጼ ምኒልክ ሃውልት ትዝታችን! –ከዳዊት ከበደ ወየሳ (አትላንታ)

$
0
0

Minilik
ሚያዝያ 27 ቀን፣ 1934 ዓ.ም. በጣሊያኖች ፈርሶ የነበረውን የዳግማዊ ሚኒልክ ሃውልት እንደገና ሲቆም፤ ቀዳማዊ ኃይለስላሴ እንዲህ አሉ።

“ይህ ዛሬ የሚመለከተን ሃውልት በ1922 ዓ.ም. በጥቅምት 22 ቀን እኛ ስንመለከተው የነበረው ነው። ለታላቁ ለኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት ዳግማዊ ምኒልክ እጅግ ከፍ ላለ ስራቸው መታሰቢያ እንዲሆን አቆምነው።ጊዜ የሚያስመሰግናቸውን ስራቸውን በዚህ ሃውልት ተመለከትንበት። የኢጣሊያ ፋሽስት የጦር ሰራዊት በግፍ አገራችንን ከወረረ በኋላ በኢትዮጵያ ባለፈው ስራቸው የታወቁትን ኢትዮጵያውያኖችን ሲያጠፉ የኢትዮጵያንም ገናናነት ታሪክ ለመደሰሰ ተጣጥሯል። በዚህም መሰረት ሃምሌ 4 ቀን፣ 1928 ዓ.ም. የአጼ ምኒልን ሃውልት ነቀለው። በዚያን ጊዜም ኢትዮጵያዊያኖች ከትልቅ እስከ ትንሹ የአይን እንባ ብቻ ሳይሆን ልቡ ያለዘነ አይገኝም። ነገር ግን ታሪክ አይደመሰም። የታላቅ ስራ መታሰቢያ ለጊዜው ከመታየት ቢሰወር ጠላት ሊማርከው አይችልም።”

የአድዋ ድል እና የአጼ ምኒልክ ሃውልት ትዝታችን!
ዳዊት ከበደ ወየሳ ከአትላንታ

ሙሉውን ለማንበብ እዚህ ይጫኑ

↧

አያስቅም! አጭር ወግ (ከክንፉ አሰፋ) ጋዜጠኛ

$
0
0

በብሄራዊ ትያትር አካባቢ አንዲት አነስተኛ ምግብ ቤት ነበረች። «ገሊላ ምግብ ቤት» ትባል ነበር። በአዲስ አበባ «ቁምራ» ከመግባቱ በፊት በአካባቢው ያሉ የመንግስት ሰራተኞች በምሳ ሰዓት ይህችን ምግብ ቤት ያጨናንቋት ነበር። ቁምራን የማታውቁ ካላችሁ፤ ለጽድቅ የሚደረግ መንፈሳዊ ጾም እንዳይመስላችሁ። እድገትና ትራንስፎርሜሽኑ ያመጣው አዲስ ክስተት ነው – ቁርስ ምሳና ራት በአንድ ጊዜ የመመገብ ዘዴ። «ኑሮ በዘዴ፣ ጾም በኩዳዴ» ይባል ነበር። ይህ አባባል አሁን መኖ በዘዴ በሚል ተቀይሯል። መቼም ሁሉም ነገር በነበር እየቀረ ነው።
ጋዜጠኛ አቤል አለማየሁ በቅርቡ ባሳተመው “የአዲስ አበባ ጉዶች” የሚል መጽሃፉ ላይ ስለዚህች ታሪካዊ ምግብ ቤትም ትንሽ ብሏል። የምግብ ቤትዋ ባለቤት “ገሊላ ምግብ ቤት” የሚለው ጽሁፍ በከፊል አጥፍተውታል። አሁን ምግብ ቤት የሚለው ተነስቶ “ገሊላ” የሚለው ብቻ ነው የቀረው። ጉዳዩ በህግ እንዳያስጠይቃቸውም ይመስላል ጽሁፉ ላይ ነጭ ቀለም ነው የደፉበት። የምግብ ቤቷ ትራንስፎርሜሽን መሆኑ ነው። የዚህ ትራንስፎርሜሽን ትርጉም የገባቸውም ሆነ ያልገባቸው ተስተናጋጆች ወደ ገሊላ (ምግብ ቤት) ጎራ ማለታቸው አልቀረም። የዚህች ቤት አዲሶቹ ደንበኞች በአነስተኛና ጥቃቅን የተደራጁ ወጣቶች ናቸው። እዚያ ሲገቡ ሰልፍ ይጠብቃቸዋል። ይህች ስፍራ ስፋትዋ ለምግብ ቤት በቂ ነበር። ለቀን አልጋ አገልግሎት ግን ትንሽ ስለጠበበች ነው ሰልፍ ሊከሰት ያቻለው። ተራ የደረሳቸው በመጀመርያ ሜኑ ይቀርብላቸዋል። የቀድሞው የምግብ ሜኑ በወይዛዝርት ፎቶ ተቀይሯል።….
ይህ ዘርፍ አሁን ከኮብልስቶንም የበለጠ አዋጭ እየሆነ በመምጣቱ፤ ምግብ ቤቶች የአገልግሎት አይነታቸውንና የሜኑ ደብተራቸውን እየቀየሩት መሆናቸው እውነት ነው።
የእድገትና ትራንስፎርሜሽን ወሬ መሰማት ከተጀመረ ትንሽ ዘገየ። ይህ አዋጅ ከተሰማ በኋላ የእርሻ፣ የኢንዱስትሪና የሃይል አቅርቦቶች በሙሉ በአስር እጥፍ ነው ያደጉት። እድገታቸው ታዲያ ወደላይ ሳይሆን እንደባህር ዛፍ ወደታች ነው። በእርግጥ የለውጥ ምልክቶች በሀገሪቱ እየታዩ ነው ከተባለ የዝሙት ኢንደስትሪው በደንብ ለመጠቀስ ይችላል። ይህ ዘርፍ በተለይ ከአረብ ሃገር የበርካታ ቱሪስቶች መስህብ ሆኗል። በዚያን ሰሞን አንድ በአዲስ አበባ የሚታተም ጋዜጣ ድንግልና በአስር ሺህ ብር እንደሚሸጥ አስነብቦን ነበር። አንዲት ደናግል ለዚህ ጸያፍ ነገር ስትዳረግ ድህነትን ብቻ አይደለም የምትሰናበተው። የማንነትዋ መግለጫ የሆነው የሞራል ጉዳይም አብሮ ይሄዳል።
የአገልግሎት ክፍያው የሚከናወነው በዶላር መሆኑ ደግሞ በዚህ ዘርፍ ላይ የግሽበት ችግር አይደርስበትም። ኢንደስትሪው ለሃገሪቱ የውጭ ምንዛሪ ምንጭም ስለሆነ ይመስላል ከመንግስት በኩል እየተበረታታ የመጣው። የውጭ ምንዛሪ በማስገኘቱም «ልማታዊ» ተግባር ተብሏል። መንግስት ከዚህ ሴክተር ምን ያህል እንደሚጠቀም በውል ባይታወቅም አገልግሎት ሰጭዎቹ (ደላሎቹ) ግን ሃብታም እንደሆኑ ይነገራል።
ወደ ጎተራ አካባቢ በተሰራው የኮንዶሚንየም መንደር ደግሞ ሌላ ታሪክ አለ። ይህ ኮንዶ «ፌስቡክ» የሚል ስያሜ ተሰጥቶታል። ለምን ፌስቡክ እንደተባለ ለማወቅ ብዙም ግዜ አይፈጅም። የቆነጃጅት ኮረዳዎች ሁሉ መሰብሰቢያ ነው። ትምህርት አቋርጠው ወይንም ከቤተሰብ ተኮራርፈው የተሰወሩ የቤት ልጆችን ለማግኘት ወላጆች ወደ ፖሊስ ጣብያ መሄድ አቁመዋል። ወደ ጎተራው «ፌስቡክ» ብቅ ካሉ የጠፉትን ሁሉ እዚያ ያገኙዋቸዋል። ባለሃብቶች እና ባለግዜዎች ወጣት ሴቶችን እየወሰዱ እዚያ እንደ እቃ ያስቀምጧቸዋል። ይህን የሚያጫውቱኝ ወዳጆቼ እየሳቁ ነበር የነገሩኝ። ነገሩ ያሳዝናል እንጂ አያስቅም!
በዚህ ልማታዊ «ቢዝነስ» ውስጥ ጨቅላዋ ማሪቱም ገብታበታለች። የማሪቱን ነገር ማንሳቱ ብቻ ሁኔታውን በደንብ ይገልጸዋል።
ይህች ጨቅላ ጉብል በወግና በማዕረግ ያደገችበትን ቀዬ ለቃ ከወጣች አመታት አልፈዋል። በሃገሬው ሹሩባ ተጎንጉኖ የነበረው ያ ዞማ ጸጉርዋ በፈረስ ጸጉር ተተክቷል። እንደምንጭ ውሃ ጥርት ብለው የነበሩት አይኖችዋ በህብረቀለማት ኩል ተበርዘዋል። በአረንጓዴ ካኪ የተሰፋላት ሽንሽን ቀሚሷ ካላይዋ ላይ ተጥሎ በዘመናዊ ሚኒ-ስከርት ተቀይሯል። ኮንጎ ጫማዋም በሂል ተለውጦ ምቾትዋን ወስዶባታል። ማሪቱ አሁን አዲስ ዓለም ውስጥ ናት። እንደ አሻንጉሊት ሁለመናዋ ሰው-ሰራሽ ሆናለች። ስምዋም ተቀይሯል። አሁን ሜሪ ናት። ማሪቱን ሜሪ ለማድረግ ደላሎቹ ችግር የለባቸውም። ዘመናዊ ልብስ እንጂ ዘመናዊ ስም ወጪ አያስወጣም። ለማሪቱ ከሜሪ ይልቅ ማርታ ወይንም መስከረም ይቀርብ ነበር። እነዚህን ሁለት እርከኖች ዘልሎ ፈረንጅኛው ላይ መሄዱ፣ ምን ያህል ፈጣን የእድገት ጎዳና ላይ መሆናችንን ያሳየናል።
እርግጥ ነው። ማሪቱ በትምህርቷ ገፍታ ሰዎች የደረሱበት ለመድረስ ችሎታውና ፍላጎቱ እንጂ አቅሙ አልነበራትም። እድሜዋ ለአቅመ ሄዋን እንደደረሰ እንደከተሜ እኩዮችዋ ለኮሌጅ ትምህርት አልታደለችም። ወላጆችዋ ብዙም ቅሪት የላቸውም። ለችግር ግዜ አስቀምጠዋት የነበረችውን ገንዘብ ለ«ህዳሴው ግድብ» መዋጮና ቦንድ መግዣ አውለዋት በተስፋ መኖር ጀምረዋል። አዎ ተስፋቸውን ሁሉ በህዳሴው ላይ አድርገዋል። ግና ተስፋ የእለት ጉርስ አይሆንም።
ሜሪ ድህነትን ለማሸነፍ ስትል የማትወደውን ስራ የመስራት ውሳኔ ላይ ደርሳለች። በውሳኔዋ እንዳትጸጸት የሚያጽናናት ነገርም አለ። «ትምህርት ምን ያደርጋል? የተማረ የት ደረሰ?» የሚለው የወላጆችዋ አባባል በእምሮዋ ውስጥ ያቃጭል ነበር። ይህንን አባባል እንደ ጥቅስ እቤትዋ ላይ ሰቅላዋለች። ከህሊና ወቀሳ ለመሸሽ ስትፈልግ ቀና እያለች ይህንን ጥቅስ ታነብና ትጽናናለች። ታላቅ ወንድምዋ የኢንጅነሪንግ ምሩቅ ነው። የዩኒቨርሲቲ ትምህርቱን እንዳጠናቀቀ ከልጅነቱ ጀምሮ ይመኝ የነበረውን ስራ ሊያገኝ አልቻለም። ይህም፣ ወላጆቹ በትምህርት እና በእውቀት ላይ ተስፋ እንዲቆርጡ አድርጓቸው ነበር። የኋላ-ኋላ ግን የስራ አጡን ጎራ ለማምለጥ አዲስ ስልት ቀየሰ። የኢህአዴግ አባልነት ፎርም ሞልቶ በጥርነፋ መያዙ ግድ ሆነበት። ከዚያም በ«አነስተኛና ጥቃቅን» ዘርፍ ተደራጅቶ ኮብልስቶን ላይ ተሰማራ። ድንጋይ ሲፈልጥና ሲሸከም ለመዋል መስፈርቱ መብዛቱ ሜሪን አምርሯታል። በመጀመሪያ የዩኒቨርሲቲ ምሩቅ መሆን፣ ከዚያ የአባልነት ፎርም መሙላት፣ ከዚያ በአነስተኛና ጥቃቅን መደራጀት፣ ከዚያ መጠርነፍ…።
በደርግ ግዜ ኑሮ መሯቸው በሱዳን ድንበር ሊጠፉ የነበሩ ወጣቶች፤ ጠረፍ ላይ ሲደርሱ አንድ መፈክር አዩ። “ትግላችን መራራ፣ ጉዟችን እሩቅ፤ ግባችን ረጅም ነው!” የሚል መፈክር። ወጣቶቹ ተስፋ ቆርጠው ጉዟቸውን አቋረጡ። ከዚያም ጫካ ገቡ ይባላል። ያሁኑ ዘመን ጫካ «ቼቺንያ» የሚባለው መንደር ነው። ሜሪም ወንድሟ ያለፈበትን ረጅም መንገድና አስቸጋሪ መስፈርቶች ማሟላት ስለሚሳናት አጭሩን መንገድ መምረጥ ነበረባት።
በተለይ ከመካከለኛው ምስራቅር የሚመጡ ቱሪስቶች፣ አየር ባየር ነጋዴዎችና ባለስልጣናትም ጎራ እያሉ የሚዝናኑባቸው ማሳጅ ቤቶች እንደአሸን ነው የፈሉት። ከታይላንድ የዝሙት እንደስትሪ የተወረሱ “ሃፒ እንዲንግ” ተግባራት የሞራል ውድቀታችን ምን ያህል እንደወረደ ያሳየናል። እንደዚህ አይነቶቹ ነውር ነገሮች ሁሉ ገቢ እስካስገኙ ድረስ አዋጭ ስራዎች ናቸው። በልማታዊው መንግስታችንም ይበረታታሉ።
ሁሉን ነገር ተነጠቀን የቀረችን አንዲት ነገር ሞራል ብቻ ነበረች። የሞራል እሴቶቻን ግን እንዴት ነው እንዲህ የራቁን? መልካም ስነ-ምግባር፣ ጨዋነት፣ ግብረ-ገብነት እና ፈሪሃ እግዚአብሄር የጠፋበት ህብረተሰብ መጨረሻው ምን ሊሆን ይችላል? ሃገር ማለት መሬት ብቻ አይደለም። ሃገር ማለት ሕዝብና አንድ ሉዓላዊ አካል ብቻም አይደለም። መልካም ስርዓት እና የሞራል እሴት የሌለው ሃገር ከማፍያ ጉረኖ የተሻለ አይሆንም።
ሌት ተቀን የምንደኖቅርበት እድገትና ትራንስፎርሜሽም የሚመጣው በመጀመርያ ሃገር ስትኖር መሆኑን መገንዘብ ይበጃል። …. የሃይማኖት አባቶችስ ይህንን እያዩ ለምን ዝም አሉ? ስራቸው ፍትሃት ማድረግ እና እና ግብር መሰብሰብ ብቻ መሆን ነበረበት? ወይንስ እነሱንም ይኸው ልማታዊ አስተሳሰብ ተጸናወታቸው?

↧

ሰሞነኛ ትዝብቶች …..

$
0
0

ግርማ ሠይፉ ማሩ
girmaseifu32@yahoo.com

ኢህአዴግ የሚባል ገዢ በሄድንበት ሁሉ ለትዝብት የሚሆኑ ነገሮችን ማስቀመጥ አይተውም እኛም አንጀታችን ማረሩ ይቀጥላል፡፡ አንዳንዶቻችን ለአንጀታችን ማረር መፍትሔ ብለን በፅሁፍ አስፍረን እንገላገላለን ያለበለዚያ ለስንቱ አውርተን እንዘልቃለን፡፡ የሚያነብ ካለ ደግሞ ማስተካከያ ይወስዳል፡፡ ለሚስተካከሉት ማለት ነው፡፡ ተጠያቂ ካለ ደግሞ እንዲጠየቅ ማድረግ የእርምጃው አንድ አካል ይሆናል፡፡ ኢህአዴግ ግን አፍ እንጂ ጆሮ የለውም ሰለሚባል ተጠያቂነት ያሰፍናል ብሎ ማመን አስቸጋሪ ነው፡፡ አባላቶቹ ሲያጠፉ ለአሽከርነት ቀብድ እንደከፈሉ ተቆጥሮ ይመዘገብና ሲፈለግ ይመዘዛል እንጂ በወቅቱ እርምጃ አይወስድም፡፡
አንድ ሰሞን የአዲስ አበባ መንገዶች ባለስልጣን ምክትል ኃላፊ የነበረ አስቻለው የሚባል ጓደኛዬ በከተማው ውስጥ መንገድ ዘግተው አጥር የሚያጥሩ ባለስልጣናትን ማሾር ጀምሮ ነበር፡፡ በዚያ መነሻ ብዙ የከተማ መንገዶች ተከፍተው መተንፈሻ አግኝተን ነበር፡፡ ባላስልጣናቱ በመንግሰት ገንዘብ ህገወጥ ግንባታ ማካሄዳቸው ከተጠያቂነት እንደማያድናቸው አስረግጦ ሲነገራቸው ማፍረስ ጀመሩ፡፡ እኛም ጉድ ተሰኝተን በቀጣይ መከላከያም ሆነ ቤተ መንግሰት የእግረኛ መንገድ እየዘጉ ማለፍ ክልክል ነው ማለት አይቻሉም ጥበቃቸውን ውስጥ ግቢያቸው ያደርጋሉ ብሎን በቴሌቪዥን መስኮት ተመለከትነው፤ ይህም ሳይተገበር እርሱም ተገፍቶ ከሀገር ወጥቶ ይኖራል፡፡ ይህን ጉድ ያስታወሰኝ በቅርቡ ቂሊንጡ እስር ቤት ሄጄ ያየሁት ጉድ ነው፡፡ አቶ አስራት ጣሴን በገደብ ከተጣለበት እስር የሚታሰብ ይሁን አይሁን ባይታወቅም በጣቢያ ለሶሰት ቀን እና በቂሊንጡ ለሰባት ቀን ቆይቶዋል፡፡ እንዳሰቡት አስራት ጣሴን አንገት ያስደፉት አልመሰለኝም ይልቁንም ውስጥ ገብቶ ተምሮ የወጣ ይመስለኛል፡፡ ብዙ ወዳጆች እንዳፈራ ነው የነገረኝ፡፡ አቶ አስራትን ለማውጣት እንደ ማስገባት ቀላል አልነበረም፡፡ የማውጣት ሂደቱም ግምገማ/ቢ.ፒ.አር ሊሰራለት እንደሚገባ የሚያሳብቅ ነው፡፡ ውስጥ ገብቼ ምን ያህል ደቂቃ እንጠብቅ ብዬ ሰሟገት ከ20 -30 ደቂቃ ቢሆን ነው ውጪ ጠብቁ ተብለን ወጥተን አላፊ አግዳሚ መታዘብ ጀመርን የተባለው ደቂቃ አለፈ ከሁለት ሰዓት በላይም ሆነ፡፡ ከቅጥር ጊቢ ውጭ ያለስራ መቀመጣችን አንድ ነገር ይዞ ብቅ አለ፤ ወዲህ ወዲያ ማየት እና መንቀሳቀስ፡፡ እየተንቀሳቀስን እያለ የጊቢው አጥር በግምት ርዝመቱ ከሁለት መቶ ሜትር እና ቁመቱ ከሁለት ሜትር በላይ የሚሆን ነው፡፡ ይህ አጥር ከጥሩነሽ ቤጂንግ ሆስፒታል ወደ ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ የሚሄደውን አዲስ መንገድ ዘግቶ ተገትሮዋል፡፡ የመንገድ ሰራውን አስቁሞታል፡፡ ይህ አጥር የተሰራው በቅርብ ሲሆን ለምን 12 ሜትር ከፕላን ወጥቶ እንደ ተሰራ ግርምት ፈጠረብኝ፡፡ ይሄኔ ነው አሰቻለው ትዝ ያለኝ መፍትሔውን ሳሰብ አጥሩ መፍረስ አለበት ግን ይህ የሚፈርስ አጥር የተገነባው በህዝብ ሀብት ነው፡፡ አሁን ባለው ሁኔታ መፍትሔው መፍረስ ብቻ ነው፡፡ ይህ አጥር በዚህ ሁኔታ ከፕላን ወጥቶ እንዲሰራ ያደረገ መጠየቅ አለበት፡፡ ከፕላን አልወጣንም የሚል መከራከሪያ ካላ ይህን ፕላን አዘጋጅቶ የሰጠ መሃንዲስ መንገድ መኖሩን አላውቅም ነበር ሊለን ስለማይችል ተጠያቂ መሆን ይኖርበታል፡፡ በማነኛውም ሁኔታ ግን የተጠያቂ ያለ ብለን እንድንጮህ ይህን ሀሳብ ላካፍላችሁ ወደድኩ፡፡ ከአጥሩ ጋር ተያይዘው የሚፈርሱ ብዙ የመብራትና ሌሎች መሰረተ ልማቶች መኖራቸውን መዘንጋት ያለብን አይመስለኝም፡፡ ለማነኛውም ይህን ፅሁፍ ያነበበ ጋዜጠኛ የእስር ቤቱንም ሆነ የአዲስ አበባ መንገዶች ባለስልጣን ሰዎቹን አነጋግሮ ለህዝብ ይፋ ያድርግልን፡፡ አንገታችን ታንቆ በምንከፍለው ግብር የሚሰራ መንገድም ሆነ አጥር እንደፈለገ የሚፈርስ መሆን የለበትም፡፡
ሌላው ሰሞነኛ ጉዳይ ደግሞ የአማራ ክልል ፕሬዝዳንት አቶ ገዱ አንዳርጋቸው ወንበራቸውን በቅጡ ሳያደላድሉ ፈተና የበዛባቸው መሆኑ ነው፡፡ አንዱ የፈተናቸው ምንጭ ደግሞ አቶ አለምነው መኮንን የተባለ ካድሬ ነው፡፡ አቶ አለምነውን አንተ ያልኩት ከተመስገን ደሳለኝ ተውሼ ነው፡፡ አምባገነን ሰርዓትን የሚመሩ ሰዎች አንተም ሲበዛባቸው ነው ሰለሚል ማለቴ ነው፡፡ ለነገሩ እኛም ሰፈር ቢሆን አንቱ ብሎ ስድብ የለም፡፡ አቶ አለምነው ደግሞ ሰድበውናል ስለዚህ መሰዳደብ ሊጀመር ከሆነ አንቱታው አይገባቸውም፡፡ ብአዴን ለአማራ ህዝብ ክብር ሲል ይህን ካድሬ ይቅርታ እንዲጠይቅ በማድረግ ከኃላፊነቱ ማንሳት ሲገባው በየቦታው እየዞረ ማስተባበሉን ቢያቆም ጥሩ ነው፡፡ ለነገሩ የዚህ ዓይነት አካሄድ በኢህአዴግ መንደር የተለመደ እንደሆነ ይታወቃል፡፡ የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ መለስ ዜናው በምክር ቤት ቀርበው ይሁን በጋዜጣው መግለጫ አንድ ፋውል መስራታቸው የተለመደ ነበር፡፡ ታዋቂዎቹ ፋውሎች ባንዲራ ጨርቅ ነው፣ የአክስሙ ሐውልት ለወላይታ ምኑ ነው? የመሳሰሉት አሁንም ትዝ ይሉናል፡፡ በዚህ ጊዜ በህዝቡ ዘንድ ጫጫታ ሲነሳ እርሳቸው ማለት የፈለጉት የግል ሚዲያ፣ የድሮ ስርዓት ናፋቂዎች፣ ኒዎሊብራሎች እንደሚሉት ሳይሆን ይህን ለማለት ነው በማለት እንደምታ ትርጉም ይስጠው ነበር፡፡ አለቆቻቸው ውሃ እየተጎነጩ የፈለጉትን ይናገራሉ፤ ካድሬዎች ምራቃቸው እስኪደርቅ በውሃ ጥም እየተሰቃዩ ለማስተባበል ይሞክራሉ፡፡ ይህ የማስተባበል ዘመቻ በፍፁም ተቀባይነት እንደሌለው መታወቅ ይኖርበታል፡፡
የክልሉ ፕሬዝዳንት አቶ ገዱ አንዳርጋቸውም ቢሆን በማስተባበል ጫወታው የገቡ ይመስላል፡፡ አቶ አለምነው መኮንን ፀያፍ ስድብ ተሳድቦዋል፡፡ ድምፁ የእኔ ነው ሰድቡ ግን የእኔ አይደለም የሚለውን ቀልድ ትቶ ማሰተባበል ካልቻለ ይቅርታ ይጠይቅ፣ ብሎም ከሃላፊነቱ ይነሳ፡፡ የአቶ ገዱ “አቶ አለምነው ለአማራ ሕዝብ ዕድገትና ብልፅግና ሌት ተቀን ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይሉ የሚሰሩ ናቸው” የሚለው ምስክርነት እውነት ከሆነ ጥፋት ማቅለያ እንጂ ከጥፋተኝነት መዳኛ አይደለም፡፡ በፍርድ ቤት ጥፋት አጥፈተሃል አላጠፋህም ተብሎ ሲጠየቅ የቤተሰብ ሃላፊ ነኝ ብሎ እንደ መመለስ ነው፡፡ አቶ ገዱ አንዳርጋቸው አሁን የያዙት ተግባር ደረጃቸውን አይመጥንም የሚጠበቅባቸው ለተሰደበው ህዝብ ተገቢውን ምላሽ መስጠት ነው፡፡ እኔ አቶ አለምነው ይሰቀል አላልኩም፤ ይውረድ ነው፡፡
ሌላኛው አስገራሚ ዜና ደግሞ ፖሊሶች ማን ፍርድ ቤት እንደደፈረ አላወቅንም አሉ፡፡ ኮምሽነር ጄነራሉም ማወቅ አልቻልምን አሉ፡፡ አሰቂኝ ዜና ነው፡፡ እኔ የገባኝ ግን ፍርድ ቤት በመድፈር ከተጠረጠሩት ውስጥ ባለ ከፍተኛ ማዕረጎች ፍርድ ቤቱን እንደደፈሩ የሚያሳይ ነው ፍንጭ ነው፡፡ ተራው ወታደር ቢሆን ኖሮ ታንቆ ይስጥ ነበር፡፡ ተራ ወታደሩ አለቆቹ እንዳጠፉ አውቆ ቢናገር ደግሞ የሚከተለውን ያውቃል፡፡ ስለዚህ ዝም ማለት መርጠዋል፡፡ ይህ ካልሆነ ደግሞ በእለቱ ተረኛ የነበሩት አስራ አምስቱም በጋራ ተባብረው ነው ያጠፉት ማለት ነው፡፡ ለጥፋታቸው የሚመጥን ቅጣት ይገባቸዋል፡፡ በነገራችን ላይ ፍርድ ቤት ባይደፍሩም ጥፋተኛ እንዲታወቅ ትብብር ባለማድረጋቸው ሁሉም ጥፋተኞች ናቸው፡፡ ዳሬክተር ጄነራሉ እንደሚሉት ጉዳዩን ወደ እኛ መልሱትና እኛ በተቋም ደረጃ እርምጃ እንውሰድ የምትለውም ፌዝ ቢጤ ነች፡፡ ለማነኛውም ግን ፍርድ ቤቱ አስተማሪ የሆነ ነገር ያደርጋል ብለን እንጠብቃለን፡፡ ይህ ጉዳይ በህዝብ ዓይን እና ጆሮ ሰር ገብቶዋል፡፡ ዘጠና ሚሊዮን ህዝብ ውስጥ ለሚደርስ ጥፋት መርምሮ እንዲይዝ የተቀመጠ አካል ከአስራ አምስት ሰዎች ውስጥ ጥፋተኛ መለየት አልቻልኩም ሲል ግን ትዝብት ውስጥ እንደሚገባ ያለማወቁ ያስተዛዝባል፡፡
በመጨረሻም ለመሰናበቻ የሚሆን ሰለ የካቲት 11 ክብረ በዓል እናንሳ፡፡ ይህ በዓል በየአምሰት ዓመት በሰፊው ይከበር የነበረ ሲሆን አሁን ግን በተለየ ሁኔታ እንደተከበረ አብርሃ ደስታ ነግሮናል፡፡ ይህ ለምን እንደሆነ ባይገባኝም ምን አልባት በቀጣይ ዓመት በምርጫ ውጥረት ምክንያት ሊሆን ቢችል ብሎ መጠርጠር የአባት ነው፡፡ ግን ምን ችግር አለው በሚቀጥለው ዓመት ደግሞ ከዚህ በበለጠ ቢያከብሩት ገንዘቡ እንደሆነ የፓርቲ እንዳልሆነ ይታወቃል፡፡ እኔ ግን ግርምት የፈጠረብኝ ኢህአዴግ አዲስ አበባን ከተቆጣጠረ በኋላ ከፍተኛ አመራሮችን(እነ ተፈራ ዋልዋን ጨምሮ) ይዞ ወደ አዲስ አበባ ሊመጣ ሲል ችግር ገጥሞት የነበረው የሱዳን አውሮፕላን ለምን ለህውሓት ብቻ መታሰቢያ እንዲሆነ ተፈለገ የሚለው ነው፡፡ የሱዳኑ ፕሬዝዳንት ይህን አሮጌ አውሮፕላን አይደለም አዲስ ጀት ገዝተው ቢሰጡን የሚበዛብን አይደለም፡፡ ምክንያቱም በነብሰ ገዳይነት ለእስር የሚፈለጉ ሰውዬ እንደፈለጉ የሚወጡበትና የሚገቡበት ሀገር ከዚያም አልፎ ክሳቸው ይነሳላቸው ብሎ የሚከራር መንግሰት ይህ ስጦታ ቢያንስ እንጂ አይበዛም፡፡ የእነ ተፈራም ነብስ የህውሓት ነብስ ነች እንዴ እረ እየተስተዋለ፡፡

↧

የማለዳ ወግ .. . ዓድዋ የእኛ …የትውልድ ኩራት !

$
0
0

* የጦርነቱ መነሻ ምክንያት …
የዓድዋ ጦርነት መነሻ ምክንያት የሆነው የውጫሌ ውል አንቀጽ 17 ሲሆን ይህ አንቀጽ የኢትዮጵያን ህልውና የሚፈታተን ሆኖ በመገኘቱ እንዲሰረዝ የተደረገው ሙከራም በጣሊያን እምቢተኝነት በመክሸፉ እንደ ነበር የታሪክ መዛግብት ያስረዳሉ።
* የጣሊያን ወረራ መሰማትና እቴጌ ጣይቱ …
የጣልያንን እምቢተኝነት ተከትሎ ሚኒስትሮች፣ የጦር አለቆችና መኳንንቱ ባካሄዱት የምክክር ጉባኤ ላይ እቴጌ ጣይቱ ብጡል «እኔ ሴት ነኝ፣ጦርነት አልወድም፣ሆኖም ግን ኢትዮጵያን የጣሊያን ጥገኛ የሚያደርግ ውል ከመቀበል ጦርነትን እመርጣለሁ ፡፡ » ሲሉ የሰጡት አስተያየት ነበር፡፡
* የኢትዮጵያው ንጉሰ ነገስት የዳግማዊ አጤ ምኒሊክ የክተት አዋጅ …
ጣሊያን ውል አፍርሶ ኢትዮጵያን ሲወርር በጉልበቱ የጀግኖችን ሃገር ሊፈታው እንደማይችል ያውቅ ነበር። ጣልያን በልዩነታችን ገብቶ ሊለያየን እቅድ አቅዶም ነበር ። ይህንንም ለማሳካት በተለያየ አስተዳደር ግዛት ለይተው በሚቆራቆሱ የጦር አበጋዞችና በንጉሱ መካከል የነበረውን የከፋ ልዩነት መጠቀም ለድል እንደሚያበቃው አልሞ መነሳቱ እውነት ነበር ። ያም ሆኖ የንጉሰ ነገስቱ መኳንንቱን ፣ ሹመኞችን እና የጦር አለቆችን ሰብስበው በመምከር ብሔራዊ ክብርን ማስጠበቁ ይቅደም አንድምታ ያለው ሃሳባቸው ተቀባይነት ያገኝ ዘንድ በሰለጠነ መንገድ ከመግባባት ላይ ደረሱ። ይህም ምክክርና ስምምነት ሁሉም በአንድነት ለነጻነትና ክብሩ ይተጋ ዘንድ ታላቅ አስተዋጽኦ ያደርግ ዘንድ ሁሉም በየስራ ድርሻው ተመድበው መስራት ጀመሩ ።
Adwavictory
መስከረም 1888 ዓ.ም ወር ላይ ንጉስ ምኒሊክ ጣሊያንን ለወረራ መዘጋጀቱን በስለላ ባለሟሎቻቸው በቅርብ አረጋገጡ። በወረራ ዝግጅቱ የተቆጡት ዳግማዊ አጤ ምኒሊክ የክተት አዋጅ እንዲህ በማለት አስነገሩ …
‹‹እግዚአብሄር በቸርነቱ እስካሁን ጠላት አጥፍቶ አገር አስፍቶ አኖረኝ፤ እኔም እስካሁን በእግዚአ ብሔር ቸርነት ገዛሁ፡፡ ከእንግዲህ ብሞትም ሞት የሁሉም ነውና ስለእኔ ሞት አላዝንም፡፡ ደግሞ እግዚአብሔር አሳፍሮኝ አያውቅም፤ ወደፊትም ያሳፍረኛል ብዬ አልጠራጠርም፡፡ አሁንም አገር የሚያጠፋ፤ ሃይማኖትን የሚለውጥ፣ በፊት እግዚአብሔር የወሰነልንን ባህር አልፎ መጥቷል፡፡ እኔም የአገሬን ከብት ማለቅ፤ የሰውን መድከም አይቼ እስካሁን ዝም ብለው ደግሞ እያለፈ እንደፍልፈል መሬት ይቆፍር ጀመር፡፡ አሁን ግን በእግዚአብሔር ረዳትነት አገሬን አሳልፌ አልሰጠውም፡፡ የአገሬ ሰው ከአሁን ቀደም የበደልሁህ አይመስለኝም፡፡ አንተም እስካሁን አላስቀየምኸኝም፡፡ ጉልበት ያለህ በጉልበትህ እርዳኝ። ጉልበት የሌለህ ለልጅህ፣ ለምሽትህ፣ ለሃይማኖትህ ስትል በሃዘንህ እርዳኝ፡፡ ወስልተህ የቀረህ ግን ኋላ ትጣላኛለህ፡፡ አልምርህም፡፡ ማርያምን ለዚህ አማላጅ የለኝም…››
* ዓድዋና የጦሩ ዝግጅት …
1926634_660764873983667_1553032877_n
የዓድዋው ጦርነት በጣልያኖች በኩል የቆየ የቀኝ ግዛት ጥማቸውን ለማሳካት ቀድሞ የተጠነሰሰ ነበር። በኢትዮጵያውያን ዘንድ ግን የጦርነት ዝግጅቱ እስከ ሰባት ወር የፈጀ እንደነበር ይነገራል። ዝግጅቱ ተጠናቆ የካቲት 23 ቀን 1888 ዓ.ም ጎህ ቀዶ እስኪጠልቅ በቀድሞዋ ትግራይ ጠቅላይ ግዛት በዛሬዋ ክልል አንድ ትግራይ ውስጥ በምትገኘው በዓድዋ ከተማ ይገጥም ዘንድ ቀኑ ደረሰ ! በዓድዋው ዘመቻ በመቶ ሺሕዎች ሆኖ የዘመተው የኢትዮጵያ ጦር ከጥቂቱ በስተቀር አብዛኛው ጦር፣ ሰይፍ፣ ጋሻና የነፍስ ወከፍ መሳሪያ ይዞ እንደ ነበር የታሪክ ድርሳናት ያስረዳሉ። ጣሊያን በአስር ሽዎች የሰው ሃይል ፣ በዘመናዊ የጦር መሳሪያና በወታደራዊ ሳይንስ የሰለጠነ አውሮፓዊ ጦር ነበርና ከፍ ባለ ስንቅና ትጥቅ ተደግፎ ወረራ መጀመሩ ይጠቀሳል።
* አንጸባራቂው የዓድዋ ድል … የጥቁሮች ድል !
የጣሊያን ጦር በጄኔራል ባራቴሪ እየተመራ ባህር ተሻግረሮ ሲመጣ የተወረረችው የኢትዮጵያውያን ጦር የሚመራው በንጉሰ ነገስት ዳግማዊ አጤ ምኒሊክ ነበር። ጀግና ብልህና አርቆ አስተዋይዋ ባለቤታቸው እትየ ጣይቱ ብጡል በዚያ ባልሰለጠነ ዘመን ስልጡን ነበሩና በባለቤታች ከሚመራው የአርበኞች ግንባር እኩል ተሰልፈው ሃገሬውን ስንቅ ትጥቅ በማስታጠቅና በማበረታታት የከፈሉት መስዋዕትነት ቀላል አልነበረም። ኢትዮጵያውያን በንጉሱ ብልህ አመራርና ክተት ብለው በህብረት ተነሱ ። ከሽኩቻና ዝብሪት ተዘፍቀው የባጁት የየግዛቱ ሹሞች እና የጦር አበጋዞችም በንጉሰ ነገስት አጤ ምኒሊክ የክተት አዋጅ ልዩነታቸውን አስወግደው በህብረት ተመሙ !
Note_20140301_223118_01-1
የካቲት 23 ቀን 1888 ዓ.ም ከ118 ዓመታት በፊት በዕለተ ሰንበት ክብሩ የተነካው አርበኛ ህዝብ ዓድዋ ላይ ቀፎው እንደተነካበት ንብ ተንቀሳቅሶ ባካሔደው ውጊያ እብሪተኛውን ዘመናዊ መሳሪያ የታጠቀ የጣሊያን ጦር ጋር ገጠመ ! ከማለዳ አንስቶ ጀንበር እስክታዘቀዝቅ ባለው ጊዜ የተካሄደው ጦርነት እልፍ አእላፍ መስዋዕት ሆነው በኢትዮጵያ ድል አድራጊነት በዓድዋ ተደመደመ !
ጣሊያን ከአንባላጌ እስከ አድዋ ተጠራርጎ እንዲወጣ ያደረገው ” የጥቁሮች ድል!” በሚል አለም ባወደሰው የዓድዋ ድል የጣሊያን መንግስት የሃፍረት ማቅን በግዱ ተከናነበ። የዓድዋ ድል በመላ በአለም ከተበሰረ በኋላ የወረራው መነሻ የሆነውን የውጫሌ ውል ፈርሶ የጣልያን መንግስት በውጫሌ ውል የነበረውን አጉል ምኞቱን ይሰርዝ ዘንድ ግድ ሆነበት ። ወራሪው በሽንፈቱ አፍሮ የኢትዮጵያን ሙሉ ነፃነት አውቆ እና ተቀብሎ የሰላም ስምምነት ያደርግ ዘንድ ተገደደ ! የስምምነት ውሉም ለአለም መንግስታት ተሰራጨ። ውሉ የደረሳቸው መንግስታት እና ሃገራት የኢትዮጵያን የተረጋገጠ ሉአላዊ መንግስትነት በውድም ሆነ በግድ ተቀብለው አረጋገጡት !
* የዓድዋ ድል በዳግማዊ አጤ ምኒሊክ ድብዳቤዎች …
ዳግማዊ አጤ ምኒሊክ የዓድዋን ድል አስመልክተው ለፈረንሣዊው ሙሴ ሞንዶን የዛሬ 118 ዓመት የጻፉለት የምሥራች ደብዳቤ እንዲህ ብለው ነበር “የምሥራች በእግዚአብሔር ቸርነት የየካቲት የቅዱስ ጊዮርጊስ ዕለት ኢጣልያንን ድል አድርጌ መታሁት፡፡ በጨረቃ ሲገሰግስ አድሮ እሰፈሬ ድረስ መጥቶ ገጠመኝ፡፡ አምላከ ኃያላን ረድቶኝ ፈጀሁት፡፡ ደስ ብሎኛል ደስ ይበልህ››
አጤ ምኒሊክ በመጋቢት 23 ቀን 1988 ዓ.ም. ለፈረንሳዊው ሙሴ ሸፍኔ በላኩለት ደብዳቤ ያቸው እንዲህ ብለዋል ‹‹… ከአላጌ ጦርነት በኋላ፣ ጣሊያኖችን ጦርነት ይቅር፣ የክርስቲያንም ደም በከንቱ አይፍሰስ፣ እርቅ ይሻላል ብላቸው እምቢ ብለው መጥተው በጥጋባቸው ዓድዋ ላይ ተዋግ ተው ድል ሆኑ፡፡ እኔ ግን በድቁርናቸው ብዛት የነዚያን ሁሉ ክርስቲያን ደም በከንቱ መፍሰሱን እያየሁ ድል አደረግኳቸው ብዬ ደስ አይለኝም፡፡ ነገር ግን በግፍ የመጡ ሰዎች ናቸውና እግዚአብሔር ግፉን አነጣጠረን…፡፡›› በማለት ያስታወቁ ሲሆን ምኒልክ ለሞስኮብ ንጉሥ ኒቆላዎስም መጋቢት 23 ቀን 1988 ዓ.ም በጻፉት ደብዳቤያቸውም ‹‹እንደ አውሮፓ ነገሥታት ሥራት ሁሉ ጠብ መፈለጋቸውን ሳያስታውቀኝ፣ እንደ ወምበዴ ሥራት ሌሊት ሲገሰግስ አድሮ ሲነጋ ግምባር ካደረው ዘበኛ ጋር ጦርነት ጀመረ፡፡ ጥንት ከአህዛብና ከአረመኔ አገራችን ጠብቋት የሚኖር አምላክ ከእኛ ባይለይ በእግዚአብሔር ኃይል ድል አደረግሁት…›› ብለው መጻፋቸው ይጠቀሳል ፡፡
* አልፋና ኦሜጋ የማይረሳው መስዋዕትነት … አልፋና ኦሜጋ በክብር ይዘከራል !

ልክ የዛሬ 118 ኛ አመት እሁድ የካቲት 23 ቀን 1888 ዓም ታላቁ የዓድዋ ድል በዓድዋ ሰንሰለታማ ተራሮች ላይ ተበሰረ ! ይህ የጥቁር ህዝብ በቅኝ ገዥዎች ከተቀዳጃቸው የዓድዋ ድል እውን እንዲሆን አቀበት የወጡ ፣ ቁልቁለት የወረዱ ፣እርጥብ የጨሰባቸው ፣ ደረቅ የነደደባቸው ፣ ከቤታ ቸው የተፈናቀሉ ፣ የቆሰሉ ፣ የሞቱ ፣ መዳረሻቸው የጠፋ ጀግኖቻችን አልፋና ኦሜጋ የማይረሳው መስዋዕትነት ነው … ይህ አንጸባራቂ ድልም እነሆ አልፋና ኦሜጋ በክብር ይዘከራል !
ልክ የዛሬ 118 ዓመት ከዘመነው የፋሽሽት ጣሊያን ጦር እና ጦር ሰራዊት በላይ የጥቁር ህዝብ ብሔራዊ ክብርና ኩራት ልቀው የታዩበት የጦርነት አውድማ ነው ! ዓድዋ !
በዓድዋ ድል እንኮራለን ! የዓድዋን ድል በክብር እናዘክራለን !
ክብር ለደሙ ለቆሰሉና በክብር ለሞቱ ሰማዕታት !
ክብር ለጀግኖቻች አርበኞቻችን !
ከብር ለእምየ ምኒሊክ ! ክብር ለእቴጌ ጣይቱ !
ክብር ለኢትዮጵያ !
እንኳን ለታላቁ የዓድዋ የድል በአል አደረሳችሁ !
ነቢዩ ሲራክ
የመረጃ ምንጮቸ :
* በታዋቂ የታሪክ አዋቂዎች ከተጻፉት የታሪክ መዛግብት፣
*ከአድዋው ጦርነት ዙሪያ ከቀረቡት የተለያዩ የታሪክ ድርሳናት ፣
* በተለያዩ በጊዜ ስለ ዓድዋ ድል ገድል ዙሪያ ከተጻፉ ጋዜጦችና መጽሔቶች ሲሆን ለአንባብያን እንዲመች አድርጌ አቅርቤዋለሁ ።

↧
↧

የአፍሪካ ቀንድ፤ ዙሪያው እሳት መሀሉ ብሶት –በፕሮፌሰር መስፍን ወልደ ማርያም

$
0
0

የአፍሪካን ቀንድ ሰሞኑን ትኩሳት ይዞታል፤ ሁኔታውን ለማብራራትና ለመተንተን ሰፊ ቦታን ስለሚፈልግ አንባቢው ራሱ እንዲያስብበት በመተው ሁነቶችን ብቻ ማቅረቡ የተሻለ ነው፤ የኢትዮጵያን የውስጥ ሁኔታ ትተን በአፍሪካ ቀንድ የሚከተሉትን የተለያዩ ግጭቶችን እንመለከታለን፤

1. በጦርነት ሁኔታ ሁኔታ ላይ ያሉ የአፍሪካ ቀንድ አገሮች፤–
.ኤርትራና አትዮጵያ
.ሰ.ሱዳንና ደቡብ ሱዳን
1. በውስጥ ብጥብጥ ላይ ያሉ የአፍሪካ ቀንድ አገሮች
.ሰ.ሱዳን በውስጥ
.ደ.ሱዳን በውስጥ
.ሶማልያ

በአፍሪካ ቀንድ ውስጥ ለጊዜው ግጭት የማይታይባቸው አገሮች ኬንያና ጂቡቲ ብቻ ናቸው፤ ኬንያ ከብሪታንያ ጋር ባለው የቆየ ትስስርና በኬንያ በሚኖሩ የብሪታንያ ሰዎች ምክንያት ጋሻ አለው፤ ጂቡቲም የቆየ የፈረንሳይ ጋሻ ቢኖረውም በአሁኑ ጊዜ አሜሪካም ተጨማሪ ጋሻ ስለሆነ የውጭ ኃይል አይደፍርም፤ ጂቡቲና ኬንያ በእውነትም እንደጌታዋን የተማመነች በግ ናቸው!

Pro Mesfin
የአፍሪካ ቀንድን ውስብስብ የፖሊቲካ ሁኔታ ለመገንዘብ አገሮቹን የሚያካትቱ ማኅበሮች ብዛት መመልከት ነው፤– የአረብ ማኅበር፤ የአሜሪካ ማኅበር፤ የፈረንሳይ ማኅበር፤ የአፍሪካ ማኅበር፤ የትኛው አገር የየትኛው ማኅበር አባል መሆኑን ብቻ ሳይሆን የየትኛው ማኅበር ተቃዋሚ መሆኑንም መረዳት አካባቢው ያለበትን ውስብስብ ሁኔታ ያሳያል፤ ኢትዮጵያ፣ ኬንያ፣ ሶማልያና ጂቡቲ የአሜሪካ ማኅበር አባሎች ናቸው ለማለት ይቻል ይሆናል፤ ጂቡቲና ሶማልያ የአረብ ማኅበር አባሎችም ናቸው፤ በዚያ ላይ አራቱም የአፍሪካ ማኅበር አባሎች ናቸው፤ የማኅበር ትርጉም ትንሽ ያሳስባል።

የአረብ ማኅበር በሰሜን ሱዳን በኩል ሌሎች የማኅበሩን አባላት ግብጽንና ሊብያን ኤርትራን (ተመልካች አባል) ይነካል፤ በሁለቱ ሱዳኖች በኩል የማእከላዊ አፍሪካና የኮንጎ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ነበልባል ይታያል፤ በተጠቀሱት የምዕራብ አፍሪካ አገሮች የሚነደው እሳት በሁለቱ ሱዳኖች በኩል አድርጎ ወደሶማልያና ወደኦጋዴን ሲዘልቅ ከግብጽና ከሊብያ የሚወጣው ነበልባልም ወደሰሜን ሱዳን ይደርሳል፤ በዚህ በእሳት በታጠረው የአፍሪካ ቀንድ ሰፈር አንድ የአሜሪካን አውሮጵላን ተመትቶ ጉዳት ሲደርስበት ሁለት ያህል ሰዎችም ቆስለዋል፤ ይህ ሁሉ በኢራቅ፣ በአፍጋኒስታንና በፓኪስታን የተከፈተውን የአሜሪካንን ‹‹በሽብር ላይ ጦርነት›› ወደአፍሪካ መሻገሩን የሚያመለክት ይመስላል።

ዛሬ በሁለቱ ሱዳኖች፣ በሶማልያና በኦጋዴን ሰላማዊ ሰዎች ምኑንም በማያውቁት ምክንያት ቤታቸው እየተቃጠለና እየፈረሰ፣ ንብረታቸው እየወደመ፣ በደሀነታቸው ላይ መፈናቀልና ስደት ተጨምሮ እየተሰቃዩ ናቸው፤ ነገ አንዳንዶቹ የአፍሪካ ቀንድ አገሮች እንደኢራቅ፣ እንደአፍጋኒስታንና እንደፓኪስታን ሉዓላዊነታቸውን ያጡ አይሆኑም ለማለት ይቻላል? ከአፍሪካ ቀንድ አገሮች ውስጥ እስካሁን ለአሜሪካ ያልገበረው ኤርትራ ብቻ ነው፤ ይህንንም ሁኔታ ለመለወጥ ኤርትራን ማባበል የተጀመረ ይመስላል።

የአፍሪካን ቀንድ ከከበበው ነበልባል ኢትዮጵያ እንዴት መውጣትና ማምለጥ ትችላለች? የውስጥ ጉዳይ አመራሩ ሳይለወጥ የውጭ ጉዳይ አመራሩ አንዴት ይለወጣል? የውጭ ጉዳይ አመራር አብዛኛውን ጊዜ የውስጥ ጉዳይ አመራር ነጸብራቅ ነው ይባላል፤ እስቲ በዚህ አስተሳሰብ እነዚህን በእሳት የተከበቡ አገሮች እንመልከታቸው፤ ከአዲሱ አገር ከደቡብ ሱዳን እንጀምር፤ ገና በሕጻንነት እሳት ነደደበት፤ እሳቱን የፈጠረው ብሶት ነው፤ አዲሱ ፕሬዚደንት እንደኢትዮጵያ የአገዛዙ ሎሌዎች በቤተ ክርስቲያንም የማይወልቅ ሰፊ ባርሜጣ አድርጎ በሱፍ ልብስ እየተንሳፈፈ በጎሣ አድላዊነት መሥራት ሲጀምር ምክትሉ ተቃውሞውን በመግለጽ ሸፈተ፤ ከሠላሳ ዓመታት በላይ ከሰሜን ሱዳን ጋር በጦርነት ሲደማ የኖረው ሕዝብ አሁን ወደሌላ የጎሣ የእርስበርስ ጦርነት ውስጥ ገባ።

ለየጎሣው ራሳቸውን በመወከል ሥልጣንን መጋራት የሚፈልጉ ሁሉ ለራሳቸው እንጂ ለሕዝብ የሚያስቡ አይደሉም፤ በመሀከላችንም ብዙ ሰዎች፣ የፖሊቲካ መሪዎች ነን ባዮችም የፖሊቲካ መብትን ጉዳይ በሚገባ ያላሰቡበት ናቸው፤ ለምሳሌ በአንድነት ፓርቲ ውስጥ ከጥቂት ዓመታት በፊት በአመራር ላይ የነበሩት ሰዎች በፓርቲው ፕሮግራም ላይ የነበረውን የግለሰብ የፖሊቲካ መብት የግለሰብና የቡድን መብት በእኩልነት ደረጃ እንዲታይ በሚል የለወጡት ይመስለኛል፤ ይህም የሆነው አቶ ግዛቸው፣ አቶ ዓሥራትና ዶር. ኀይሉ አቶ ስዬንና ዶር. ነጋሶን ለመያዝ ሲሉ ነው፤ ግለሰብ የሚያዝ፣ የሚጨበጥ ፣ግዙፍ አካል ያለው ነው፤ ቡድን የፈቃደኛች ግለሰቦች ስብስብ ነው፤ ግለሰቦች ሲገቡና ሲወጡ ይለዋወጣል፤ ግለሰቦች ሳይስማሙ ሲቀሩ ይፈርሳል፤ ግለሰቦች ተስማምተው ዓላማቸውን ሲለውጡ ይለወጣል።

በጎሣ ማኅበረሰብ ውስጥ ብጥብጥ የሚፈጠረው በብሶት ነው፤ ብዙውን ጊዜ የሥልጣን ጥሙን ያላሙዋላ ጎሠኛ በድንገት ጎሣው ከረጢት ውስጥ ይገባና የሙጥኝ ይላል፤ የግሉን ሥልጣን ማጣት ብሶት ወደጎሣው የሥልጣን ማጣት ብሶት ይለውጠውና የፖሊቲካ እንጀራውን መጋገር ይጀምራል፤ በእንደዚህ ያለ የግለሰብ ብሶት የጀመረ መሬት እነዚህን ጎሠኞች ብቻ ሳይሆን፣ ጎሣቸውንም፣ አገሩንም መከራ ውስጥ ይከታሉ፤ ቆስቁሰው እሳት ያነዳሉ፤ የሚቃጠልላቸው ሲጠፋም ራሳቸው እየነደዱ ያልቃሉ፤ ለምሳሌ በኢትዮጵያ ውስጥ የጎሣ እሳትን የሚቆሰቁሱትን ሰዎች ብንመለከት አብዛኛዎቹ ከሕዝቡ ጋር እየኖሩ ሲጠቃና ሲበደል ሲጮሁለት አይደሉም፤ በየፈረንጅ አገሩ ያገኙትን እየቃረሙ ራሳቸውን ያበለጸጉና በተደላደለ ጡረታ ሠላሳና ዓርባ ሺህ ብር በወር የሚያገኙ ናቸው፤ ለጎሣ መቆርቆር በስተርጅና ሥራ ሲጠፋ የተፈጠረ ፐሮጄክት ነው፤ በሥልጣን ላይ ላሉትም ቢሆን ጥልቅ ሕንጻ ሠርቶ በአምስት ሺህ ዶላር ማከራየት የራስን የሥልጣን ብሶት ወደጎሣ ብሶት በብልጠት በመለወጥ የተገኘ የፖሊቲካ ጥቅም ነው።

የአፍሪካ ቀንድ ሕዝብ እስካልነቃ ድረስ፣ ለራሳቸው ጥቅም የሻረ የጎሣ ቁስል የሚያሹትንና በእውነት ለአጠቃላይ የአገር ጥቅም የሚሠሩትን ለይቶ ካላወቃቸው የጀመረው እሳት እየተስፋፋ የእልቂት ዘመን እንደሚያመጣ መገንዘብ የሚያሻ ይመስለኛል።

↧

ከአውሮፕላኑ ጠለፋ በኋላ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ም/ሥራ አስኪያጅ ካፒቴን ደስታ ዘሩ ለቀቁ

$
0
0

Desta Zeru Ethiopian captain

በአንድ ጎሳ እና ቋንቋ አመራር ስር ወድቋል በሚልና በዘረኝነት ሰራተኞቹን ፍዳቸውን እያሳየ ነው በሚል የሚተቸው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ምክትል ስራ አስኪያጅ እና የበረራ ክፍል ሃላፊ የሆኑት ካፒቴን ደስታ ዘሩ ስልጣናቸውን መልቀቃቸውን የኢትዮጵያ የሽግግር ምክር ቤት ምንጮቹን ጠቅሶ ለዘ-ሐበሻ በላከው መረጃ አስታወቀ። እንደ ሽግግር ምክርቤቱ ዘገባ የስልጣን መልቀቂያው ጉዳይ ግልጽ ምን እንደሆነ አይታወቅም።

ሌሎች ምንጮች የኢትዮጵያ አየር መንገድ አውሮፕላን ተጠልፎ ወደ ስዊዘርላንድ በረዳት ካፒቴን ሃይለመድህን አበራ ካረፈ በኋላ በአየር መንገዱ ውስጥ በተነሳው አለመግባባት ሊሆን ይችላል የሚሉ አስተያየቶችን እየሰጡ ይገኛሉ።

ምንጮቹ የአየር መንገዱ አብራሪዎች በቂ እውቀት እና ችሎታ እያላቸው ከውጪ አብራሪዎችን በማስመጣት ለኢትዮጵያውያኑ እድገት እና የበረራ ፍቃድ መከልከል እንዲሁም አላስፈላጊ የሆነ መንግስታዊ የደህንነት ወከባ እና የአይነ ቁራኛ ጥበቃ በአብራሪዎች ላይ ከመደረጉም በላይ የስራ መብቶቻቸው እና የሰብአዊ መብቶቻቸው በዘረኝነት ላይ የተመረኮዘው የአየር መንገዱ ማንጅመንት እንደማያከብርላቸው እነዚሁ ምንጮቹ አክለው የሚገልጹ ሲሆን፤ በወያኔ ፈጠራ ረዳት አብራሪው ሃይለመድህን አበራን “የአእምሮ በሽተኛ ነው” በሚል የተወራው ወሬም በአየር መንገዱ የሚበሩ ሰዎች ቁጥር እንዲቀንስ ምክንያት እየሆነው እንደሆነም ምንጮች ይናገራሉ።

↧

ፖለቲካዊ ቁርጠኝነት ለችግሮቻችን የመፍትሄው ቁልፍ

$
0
0

ከገለታው ዘለቀ

የሃገራቸው ነገር ሲነሳ የሚከነክናቸው ወገኖቻችን ኢትዮጵያ ላለባት ችግር መፍት ሄው ምንድነው? እያሉ ኣጥብቀው ሲጠይቁ ይደመጣል። መፍትሄውም ብቻ ሳይሆን ችግሩ ማለትም እውነተኛው ችግር የት ላይ ነው ያለው? ብለውም ኣጥብቀው ሲደመሙ ይታያል። በዛሬዋ ኣጭር ጽህፌ በነዚህ መራራ ጥያቄዎች ዙሪያ ቁንጥል ኣሳብ ለማቀበል ኣስቢያለሁ።

በርግጥም ሁላችን ኢትዮጵያዊያን የሆንን ችግሩ ምንድነው? ብለን ከጠየቅን ኣንዳንዶች ሊገረሙብን ይችላሉ። የችግሩ ተካፋይ ሆነን ሳለ፣ እየተጉላላን ያለነው እኛው ሆነን ሳለ፣ እንደገና መልሰን የሃገራችን ችግር የት ጋር ነው? ብለን ስንጠይቅ የምናወጋቸው ሰዎች ምናልባትም ግራ ሊጋቡ ቢችሉ ኣይደንቅም። ነገር ግን መጠየቃችን ትክክል ነው።

በመጽሃፍ ቅዱስ ውስጥ ትንቢተ ዳንዔል ላይ ኣንድ ናቡከደነጾር የተባለ ንጉስ ኣንድ ጊዜ ጠቢባንን ጠርቶ የህልም ፍቺ ይጠይቃል። ጥበበኞቹም ህልሙን ንገረንና ፍቺውን እንነግርሃለን ሲሉት ህልሙ ጠፍቶብኛል ስለዚህ ህልሙንም ፍቺውንም ውለዱ ብሎ ጉድ እንዳፈላ እናነባለን።
እኛ ኢትዮጵያዊያን የዋናው ችግር ተጽእኖዎች የየእለት ኑሮኣችንን ሲያምሱት ብናይም ዋናውን የችግሩን ምንጭ መፈለጋችን ግን ኣሁንም ትክክል ነው።
Bahr dar 6
የሃገራችንን ዋና ችግር የት ጋር ነው ብለን ኣጥብቀን ከጠየቅን በርግጥ የስርዓት ችግር ነው ወይ? ስርዓት በማጣታችን ነው ወይ የከፋ ችግር ላይ የወደቅነው? ብለን እንጠይቃለን። በዚህ ኣገባብ ስርዓት ስንል የኣይዲዮሎጂውን ጉዳይ ሳይሆን ፍትህና ተጠያቂነት፣ ግልጽነትና የህዝብ የበላይነት የሚንሸራሸርበት ሲስተም ተዘርግቷል ወይ ብሎ የመጠየቅ ያህል ነው። ስለ ስርዓት ስናነሳ ደግሞ በዋናነት የሚታየው ህገ- መንግስታዊ ስርዓቱ ነው። ህገ-መንግስታዊ ስርዓቱ ምን ያህል ለዜጎች ይጨነቃል፣ ምን ያህል ለፍትህና ለነጻነት ለህዝቦች ጥቅም መንሸራሸሪያ ይህናል? ብለን እንድንጠይቅ ያደርገናል። በዚህ ረገድ በርግጥ መሻሻል ያለባቸው ጉዳዮች ቢኖሩም በዋናነት ግን ችግራችን የስርዓት ችግር ሆኖ ኣናይም። ለኣብነት የ1955ቱን ህገ መንግስት ስናይ የፕሬስ ነጻነትን ይሰጣል፣ እኩል የህግ ከለላ ይሰጣል፣ የመሰብሰብ፣ ሰልፍ የማድረግ መብትን ሁሉ ይሰጣል። የደርጉም ቢሆን ለዜጎች የሚጨነቅ ኣይነት ነው። “ኢትዮጵያዊያን በህግ ፊት እኩል ናቸው” ይላል። ከሁሉ በላይ ደግሞ የ1995ቱን ስናይ “ሰብዓዊ መብቶችና ነጻነቶች ከሰው ልጅ ተፈጥሮ የሚመነጩ የማይጣሱና የማይገፈፉ ናቸው” ብሎ እጅግ ኣጠንክሮ ለዜጎች መብት መቆሙን ይደነግጋል። በውነቱ ይህ ኣንቀጽ ብቻውን ለኛ ለኢትዮጵያዊያን ዋስትና ይሆን ነበር። ይሁን እንጂ ተግባራዊው እውነት ደግሞ ለብቻው በተቃራኒው ተንሰራፍቶ ይታያል። ይህ ለምን ሆነ? እንዴት እንዲህ ሊሖን ይችላል? ብለን ነው መጠየቅ ያለብን። እንዲህ ስንጠይቅ የችግሩ ዋና ጉዳይም የስርዓት እጦት ሳይሆን ሌላ ጉዳይ መሆኑን እንረዳለን። በርግጥ ለወደፊቱዋ ኢትዮጵያ የተሻለ ስርዓት ማምጣት ያስፈልጋል። በተለይም ብዙህነቱዋን ተንከባክቦ የሚይዝ ማህበራዊ የፖለቲካ ስርዓት ያሻናል። ያ ማለት ግን ከችግራችን እንድንወጣ ብቻውን ዋስትና ነው ማለት ኣይደለም። የቱንም ያህል ጥሩ ስርዓት ዘርግተን ከችግራችን ሳንወጣ ልንቆይ እንችላለን። ርግጥ ነው የማንነት ፖለቲካ ማህበራዊ ቀውስን ያመጣ ችግሮች የበለጠ እንዲነዱ የሚያደርግ ጉዳይ በመሆኑ ከዚህ መንግስት ውድቀት በሁዋላ ከዚህ የፖለቲካ መዋቅር መውጣታችን ለመፍትሄ ትልቅ በር ኣለው። ይሁን እንጂ ኣሁንም ቢሆን የቱንም ያህል ቆንጆ ስርዓት እናምጣ ኢትዮጵያን ከመከራና ከርሃብ የሚያወጣት እሱ ብቻውን ኣይደለም። ታዲያ ምንድነው? የሚል ጥያቄ መምጣት ኣለበት። ኣዎ፣ ዋናው የሃገራችን ችግር ያለው የፖለቲከኖች ስብእና ተክለሰውነት ወይም ፐርሰናሊቲ ጋር የተገናኘ ነው።

ሃገራችን ከችግር እንድትወጣ ከተፈለገ የፖለቲካ ቁርጠኝነትን ይጠይቃል። የችግሮቻችን ቁንጮም የፖለቲካ ቁርጠኝነት እጦት ነው ብሎ መደምደም ይቻላል።የፖለቲካ ቁርጠኝነት ስንል ኣንድ ፓርቲ ስልጣን ከያዘ በሁዋላ የፍርድ ቤቱን ልጓም ለቀን መልሶ ከበላንም ይብላን፣ በራሳችን ላይ ይፍረድብን፣ ብሎ በራስ ላይ የመወሰን ኣቋም ነው። ወታደሩን ኣገርህን ጠብቅ የፓርቲ ጠባቂ ኣይደለህም ኣንተ ኣገር ጠባቂ ነህ ለማለት የፖለቲካ ሰዎችን ቁርጠኝነት ይጠይቃል። ፖሊሱን፣ ባንኩን፣ ሚዲያውን ሁሉ ልጓሙን ለቆ በሙያህ ኣገልግል ብሎ መወሰን ሲቻል ነው ከገባንበት ኣረንቋ የምንወጣው። የናፈቀንን ዴሞክራሲ በህይወት የምናየው። ጥያቄው ይህ የፖለቲካ ቁርጠኝነት እንዴት ሊመጣ ይችላል ነው። የፖለቲካ ቁርጠኝነት ከጥቂት የፖለቲካ መሪዎች ከራስ ጥቅምና ዝና በላይ የህብረተሰብን ዝናና ጥቅም በተጠሙ ሰዎች ሊነቃነቅ ይችላል። ኣንድ ቁርጠኛ መሪ ኣገር ሊለውጥ ይችላል። በታሪክ የታዩ ኣንዳንድ ቁርጠኛ መሪዎች በየሃገሩ ተነስተው ጥሩ መሰረት እየጣሉ ኣልፈዋል። በሃገራችንም የተጠማነው ይህንን ነው።

በኣሁኑ ጊዜ ተቃዋሚው ክፍል መንግስትን ኣጥብቆ ማውገዙ ትክክል ነው። የህዝቡም ልብ ነጸብራቅ ነው። ይሁን እንጂ ይህ መንግስት በማንኛውም መንገድ ሲወድቅ ስልጣን ይዞ ጥሩ ስርዓት መዘርጋቱ ብቻ ሳይሆን የፖለቲካ ቁርጠኝነት (political commitment) ያላቸውን ሰዎች ይዘዋል ወይ? ብለን እንድናስብ ያደርገናል። በዚህ ረገድ ተቃዋሚው ጥቃቅን በሆኑ ፖሊሲዎች ከመከፋፈል ይልቅ ወደ ጋራ እያመሩ ከሁሉ በላይ የፖለቲከኞችን ስብእና የመገንባቱ ላይ ማተኮር ለነገይቱ ኢትዮጵያ ዋስትና ይሆናል። ይህን ስብእና ወይም ተክለሰውነት የመገንባት ስራ ፓርቲዎችን ቢዚ የሚያደርግ ወቅታዊ ስራ መሆን ኣለበት። ኢትዮጵያ በኣሁኑ ደረጃዋ ጥቃቅን ፖሊሲዎችን በማነጻጸር የምታማርጥበት ጊዜ ላይ ኣይደለችም። መሰረታዊ የሆኑ ጉዳዮችን ያጣች በመሆኑዋ የስካንዲኒቪያው ኣይነት ዴሞክራሲ ይሻልሻል የኣሜሪካው ኣይነት? ማለቱ ያልበላትን የማከክ ያህል ነው። ሁሉቱም ሆኖላትስ ነው?
ዋናው በኣሁኑ የኢትዮጵያ ነባራዊ ሁኔታ ጉዳይ ፓርቲዎች እኔ እሻላለሁ ለማለት ዋናው መመዘኛቸው የተሰባሰቡት በተለይም ኣመራር ላይ ያሉት ግለሰቦች የፖለቲካ ቁጠኝነት ኣላቸው ወይ? ቁርጠኝነት በሞላቸው ሰዎች ቁጥር የትኛው ፓርቲ ያይላል? የሚል ልብ ያለው ድጋፍ ነው በተግባር የሚታየው ወይም መታየት ያለብት።

በቲየሪ ደረጃ በኣሁኑዋ ኢትዮጵያ በፍርድ ቤት ጉዳይ መንግስት ጣልቃ ኣይገባም። ይሁን እንጂ በተግባር ይገባል። ይገባል ብቻም ሳይሆን ፍርድ ቤት የፖለቲካ መሳሪያ ነው። ኣሁን እዚህ ጋር የጎዳን የስርዓቱ ወይም የኣሰራሩ ጉዳይ ሳይሆን መከራ ውስጥ የከተተን ጉዳይ የግለሰቦች ስብእና ጉዳይ ሆኖ ነው የምናየው። ለምን እነዚህ ግለሰቦች ስርዓቱን ይጥሳሉ፣ ህጉ ለምን ኣቅም ያጣል? ካልን የፖለቲከኞቹ ላእላይ ስብስብ በተለያየ የግል ጥቅማጥቅም የተተበተበ በመሆኑ ነው። ድህነታችንም ኣንዱ ኣስተዋጾ ያደረገ ይመስላል። የተሻለ ስራ ለማግኝነት፣ ከድህነት ለመላቀቅ፣ ፖለቲካን መሳሪያ ማድረጉ የተለመደ መሆኑና ወደዚያ ጠጋ ያሉ ሃላፊዎች በዚህ ሞቲቭ የተሞሉ ስለበዙበት ስርዓቱ በቁሙ እንዲሞት ኣድርጎታል።

ባለፈው ጊዜ ኢትዮጵያ ብሄራዊ እርቅ ኮሚሽን ማቋቋም ያስፈልጋታል የሚል ኣንድ ኣርቲክል ጽፌ ነበር። በርግጥም በኣሁኑ የነጻነት ትግል ኣሰላለፍ በኩል ጎድሎ የታየው ይሄ ነውና ይህንን ማቋቋም ተገቢ ነው። ይህ ኮሚሽን ፓርቲዎችን እያበራታታ ይህን ተፈላጊ ስብእና በመገንባቱ ረገድ ከፍተኛ ኣስተዋጾ ያደርጋል። ፓርቲዎችን በማቀራረብ ረገድ፣ የመፍትሄ ኣሳቦችን በማጠናቀር ረገድ፣ ለኣዲሲቱዋ ኢትዮጵያ የሚሆነውን ኣዲስ ሰውነት በመጠቆሙ ረገድ ከባድ ሚና ሊጫወት ይችላል። ከዚያ በተረፈ ደግሞ እኛ ተራ ዜጎች መሪዎቻችንን የማጎልበትና ወደ ህብረት የመግፋት እንዲሁም ስብእናቸውን የመገንባት ሃላፊነት ኣለብን።

የብዙ ኣፍሪካ ሃገሮች ችግር ይሄ ይመስለኛል። ታግለን በብዙ መስዋእትነት ኣንድ ኣምባገነን ከጣልን በኋላ መልሰን በሌላ ኣምባ ገነን እንተካለን። ሌላው ኣለም እየተሻሻለ ሲሄድ ይሄኛው ክፍለ ኣለም ወደ ኋላ የቀረበት ትልቁ ምክንያት የነጻነት ታጋዮች ራሳቸው በሚገባ ለኣመራር የሚበቃ ስብእና ሳያዳብሩ ወደ ስልጣን ስለሚመጡ ነው።ደቡብ ሱዳን ለዚህ ጥሩ ምሳሌ ናት። ለብዙ ኣመታት የነጻነት ትግል ታግለው፣ ብዙ ደም በመፍሰሱ ዓለም ሁሉ እነዚህ ሰዎች ቢገነጠሉ ይሻላል ብሎ ፈርዶላቸው ተገነጠሉ። የዳርፉሩን እልቂት የማያውቅ፣ ያልሰማ ያለም ክፍል የለም። ያ ሁሉ ሆኖ ኣዲስ ኣገር ከመሰረቱ በኋላ ገና ኣንድ ጊዜ እንኳን ምርጫ ሳያካሂዱ፣ በህዝብ የተመረጠ መንግስት ሳይመሰርቱ፣ ከሁለት ዓመት ያልዘለለ እድሜ ያላትን ኣገር በጎሳ ከፋፍለው ማመስ ጀመሩ።

ያለ መታደል ሆኖብን በኣንዳንድ ኣፍሪካ ሃገራት የሚነሱ መሪዎች ስልጣን ላይ ከመጡ በሁዋላ ሁለት ነገር በጣም ይወዳሉ። ኣንደኛው ዝና ሲሆን ሁለተኛው ገንዘብ ነው። ሁለቱም እጆቻቸው ይዘዋል። ባንዱ ስልጣን በሌላው ገንዘብ። ዝናውን ወደው ገንዘቡን ችላ የሚሉ ቢሆኑ ትንሽ ይሻል ነበር። ነገር ግን ሁለቱንም በሃይል ስለሚወዱና ለዚህ የተሰጠ ስብእናቸው በውስጣቸው ስላልሞተ ክብ በሆነ ችግር ውስጥ እንድንወድቅ ኣድርጎናል።ኢትዮጵያዊያን በዚህ ላይ ልንነቃ ይገባናል። በተለይ የፖለቲካ ሰው መሆን የፈለጉ ወገኖቻችን፣ መሪ መሆን የሚሹ ወገኖቻችን በየጊዜው የባህርይ ለውጥ እያሳዩ በኣመለካከትና በሃላፊነት ስሜት እያደጉልን እንዲሄዱ እንሻለን። ከፍ ሲል እንዳልኩት እኛ ተራ ዜጎች ከውጭ ሆነን መፍረድ ብቻ ሳይሆን መሪዎቻችንን መንከባከብና ፍቅርን ክብርን ማሳየት ለፖለቲካ ቁርጠኝነታቸው ሃይል ይሰጣል።

እግዚአብሄር ኢትዮጵያን ይባርክ!
geletawzeleke@gmail.com

↧

የዩናይትድ ስቴት የዉጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት በኢትዮጵያ ዉስጥ ከፍተኛ የሰብዓዊ መብት ጥሰት እንዳለ ይፋ አድርጓል (ዜና ትንታኔ)

$
0
0

John Kerry
ዋሽንግተን ዲሲ፤ የካቲት 20/2006 (ቢቢኤን) ፦ የዩናይትድ እስቴስ የዉጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት (State Department) ባወጣዉ የዘንድሮ የሰዓዊ መብት ሪፖርት ላይ የኢትዮጵያ መንግስት ያከናዉናቸዋል ያለዉን የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች በመዘርዘር ሰፋ ባለ መልኩ አቅርቦታል።
ቀድም ሲል ኢትዮጵያ ዉስጥ በ2003 በተደረገዉ ምርጫ፤ በሟቹና በቀድሞው ጠቅላይ ሚንስቴር መለስ ዜናዊ ይመራ የነበርዉ ኢ.ህ.አዴ.ግ ከ547 የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መቀመጫ 545 መቀመጫዎች አሸንፏል መባሉን ሪፖርቱ እያመላከተ የምርጫ ጣቢያዎች በመንግስት ሐይላት ቁጥጥር ስር እንደነበሩና አለምአቀፍ ታዛቢዎች ስራቸዉን በተገቢዉ መልኩ እንዳያከናዉኑ ገደብ እንደነበረባቸዉ ይገፃል።

በአገሪቱ ዉስጥ ባለዉ ከፍተኛ የመብት ረገጣ ሳቢያ ዜጎች የመሰብሰብ፣የመደራጀት፣የመናገር መብትን በገሃድ እንደሚነፈጉ የዉጭ ጉዳይ መስሪያ ቤቱ ያስደረግቸዉን ጥናቶች ተመርኩዞ ያብራራል። እነዚህን የዲሞክራሲ እሴቶችን ለመተግበር የሚሞክሩም ይታሰራሉ፣ይንገላታሉ፣ይዋከባሉ፣ዛቻ ይደርስባቸዋል፣ ክብራቸዉ ተነክቶ እንዲሸማቀቁምይደረጋሉ በማለት ሪፖርቱ ያትታል።እርዳታን የሚያስተባብሩ፣ እርዳታን ለጋሽ የሆኑ ድርጅቶች፣ ማህበራዊና ትርፍ አልባ የሆኑ ተቋማት (NGO) የግብረ-ሰናይ ተልእኮ አቸዉን እንዳይፈጽሙ የኢትዮጵያ መንግስት እንደሚከለክል፤ በሰዎች ላይ ህገ ወጥ የሆነ ግድያ እንደሚፈጽም፣ዜጎች ግርፋት-ድብደባ እንደሚደርስባቸዉ፣ ወጥ የሆኑ የማሰቃያ ተግባራት በመንግስት ሐይላት እንደሚፈጽምና በአገሪቱ እስርቤት የሚገኙ ታሳሪዎችን ህይወት ለአደጋ የሚያጋልጹ አሳቃቂ ተግባራትም እንዳሉም በሪፖርቱ ላይ ተገልጿል።

ሰዎች በፍርድ ቤት ሳይበየንባቸዉ በጅምላ ተይዘድዉ ይታሰራሉ፤በፍርድ ቤት የአሰራር ዘይቤም ይሁን በፍትህ ሒደቱ ዉስጥ ግልጽ የሆነ ፖለቲካዊ ጣልቃ ገብነት አለበት፤ ፍርድ ቤቶችም ደካማ ናቸዉ! ሲል ሪፖርቱ ይደመድማል። መንግስት ሀሳብን በነጻነት ለመግለጽ የሚሞክሩ ያገሪቱ ዜጎች ላይ ጭካኔ የተሞላበት እርምጃ እንደሚወስድ በዝርዝር የተቀመጠ ሲሆን፤ በነሐሴ 2/2005 የኢድ-አልፈጥር በዓል በሚከበርበት ወቅት፤ በሰላማዊ መንገድ ተቃዉሞ ያሰሙ ከነበሩት ሙስሊም ኢትዮጵያዉያን መካከል ከ 1000 በላይ የሚሆኑት በጅምላ ተግበስብሰዉ መታሰራቸዉና ከመካከላቸዉም የሞቱ መኖራቸዉ በሪፖርቱ ላይ አጽንኦት ተሰጥቶታል።የዜጎች ግላዊ መብትን በመግፈፍ፤ በሙስሊሙ ማህበረስብ ላይ ህገወጥ የሌሊት ፍተሻዎችም ተደርገዋል። ግልጽና ስልታዊ በሆነ መልኩም ከቦታ ወደ ቦታ ዜጎችን የማፈናቀል መርሃግብር በመንግስት መፈጸሙን የሚያስረዳዉ ሪፖርት ነጻ መሆን የሚገባዉ የመማርና የማስተማር ሒደት የመንግስት ጣልቃገብነት እንዳለበትም ይገልጻል።

ዜጎች ዲሞክራሲያዊ መብታቸዉን ተጠቅመዉ በነጻነት መንግስትን የመቀየር አቅማቸዉ ሆን ተብሎ የተገደበ ነዉ!በፖሊስ፣በፍርድ ቤቶችና በመንግስት አመራር ዉስጥ በስልጣን መባለግ-ሙሰኝነት-ጉቦኝነት በገሃድ ይተገበራሉ። መንግስት በስልጣን የባለጉንና የህዝብን አደራ ያጎሳቆሉ ወንጀለኞች ችላ በማለት ፖለቲካዊ ዉለታን ይዉላል፤ ፖለቲካዊ ምህረትን ለምግባረ ብልሹ የመንግስት አካላት እንደሚያደርግ የዩናይትድ እስቴትስ የዉጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት ሪፖርት ያጋልጻል።

በኢትዮጵያ ህገ መንግስት የጾታ እኩልነት የተረጋገጠ ቢሆንም በመንግስታዊ የአሰራር መዋቅር ዉስጥ ሴቶች ይጨቆናሉ። ህገወጥ የሆነ የሰዉ ዝዉዉር ይፈሰማል፣ የአካል ጉዳተኞች (የተሳናቸዉ) ማህበራዊ ጭቆና ይደርስባቸዋል፣የ ኤች.አይ.ቪ ኤድስ ህሙማን ማህበራዊ የሆነን በደል ይጋፈጣሉ፣የሰራተኖች መብት የተገደበ በመሆኑ ህፃናትን አስገድዶ የጉልበት ስራ ማሰራቱ የተለመደ መሆኑ በሪፖርቱ ላይ ተዘርዝሯል።

የመንግስት ሐይላት የሰዎችን ደብዛ ያጠፋሉ፤ የሰዎች መሰወር ይስተዋላል! በትግራይ ክልል በአላማጣ ከተማ መንግስት በልማት ስም ቤቶችን በሚያፈርስበት ወቅት አለመግባባት ተፈጥሮ የታሰሩ 12 የአካባዊ ተወላጆች የገቡበት እንደማይተዋቅ እና ተመሳሳይ በሆነ መልኩ በሶማሌ ክልል ያለዉ ልዩ የፖሊስ ሐይል በክልሉ ተወላጆች ላይ ኢሰብዓዊ የሆነ ማንገላታት፣ማሰቃየት፤ ግድያ እደሚፈጽም መታወቁ ተገልጿል።

የኢትዮጵያ ህገመንግስት ቶርቸር (ግርፋት ድብደባ ማሰቃየት)ይከለክላል። ቶርቸርን የመሰሉ የሰዉ ልጅን ክብር ገፋፊ የሆኑ ጭካኔ የተሞላባቸዉ ተግባራት፤በመንግስት የደህነነትና የጥበቃ ሐይላት እንደሚፈጸሙ በማጋለፅ በጥር 9/2005 የተያዘዉ የሙስሊሞች ጉዳይ መጽሔት አምድኛ እና ማኔጂንግ ኢዲተር የነበረዉ ጋዜጠኛ ሰለሞን ከበደ በማእከላዊ የምርመራ ማእከል ዉስጥ በተደጋጋሚ የዚሁ ህገወጥና አስከፊ ተግባር ሰለባ እንደነበር በዩናይትድ እስቴት የዉጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት ሪፖርት ላይ በዋቢነት ተጠቅሷል።

በጥቅምት 8/2006 ሁማን ራይትስ ዎች ያወጣዉን ሪፖርት እንደ አብነት በመጥቀስ በመጥቀስ በማእከላዊ የምርመራ ማእከል ዉስጥ መርማሪዎች ታሳሪዎችን በማስገደድ የእምነት ቃል እንደሰጡ እንደሚያደርጉ የዩናይትድ እስቴትስ የዉጪ ጉዳይ መስሪያ ቤት እየገለጸ፤ በማእከላዊ እስር ቤት ዉስጥ ከፍተኛ የሆነ ቶርቸር (ግርፋት-ድብደባ-ማሰቃየትት)፣ ዛቻ፣ማስፈራራርት፣ እስረኞች ላይ ዉሃ መድፋት፣የእስረኞችን እጅ ጣራ ላይ አስሮ ለረጅም ሰዓታት ማቆም፣እሰረኞችን ነጥሎ ለብቻ ማሰርን የመሳሰሉ ኢሰብዓዊ ተግባራት እንደሚፈጽሙና ዲፕሎማቶች፣ኤንጂኦ (በጎ አድራጊ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ትርፍ አልባ ድርጅቶች) እስረኞችን የመጎብኘት ፍቃድ እንደሚነፈጉ ተገልጿል።

በመስከረም 2005 በተገኘዉ መረጃ መሰረት ከ70,000 እስከ 80,000የሚድርሱ እስረኞች መኖራቸዉ ሲታወቅ፤ ከነዚህም መካከል 2500ሴቶች ሲሆኑ 600 ህጻናት ከእናቶቻቸዉ ጋር መታሰራቸዉ እና ታዳጊ ወጣቶች ከአዋቂዎች ጋር አብረዉ እንደሚታሰሩ ተዘግቧል። የአገሪቱ እስር ቤቶች በጣም የተጣበቡ ከመሆናቸዉም ባሻገር ወታደራዊ ተቋማትም እንደ እስር ቤት ማገልገላቸዉ ተዘግቧል። በርካታ እስረኞች ከመጣበብ፣ተነጥሎ ከመታሰር፣ የተማሏ የጤና ግልጋሎት ካለመኖሩ የተነሳ ለአእምሮ ህመም ይዳረጋሉ። ለአንድ እስረኛ የምግብ፣ የዉሃ አቅርቦትን ለመለገስ እና የጤና ግልጋሎት ለመስጠት በቀን ስምንት ብር ከአስር ሳንቲም ብቻ እንደተመደበ የዩናይትድ እስቴትስ የዉጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት አመታዊ የሰዓዊ መብት ሪፖርት ይዘረዝራል።

ኢትዮጵያዉያን ሙስሊሞች ከ2004 ጀምሮ ሰላማዊ የሆነ ተቃዉሞን በአወሊያ የትምርት ተቋም ዉስጥ በመጀመር ከአርብ ስግደት (ከጁመዓ ሶላት) በሗላ በቀጣይነት የተቃዉሞ መርሃግብር እንደሚያከናዉኑና፤ ይህ የቅዋሜ ተግባር ምንም ሰላማዊ ቢሆንም የፖሊስ አካላት ሰዎችን በመያዝ አላስፈላጊ ሐይል እንደሚጠቀሙ ሪፖርቱ ያስረዳል። በሐምሌ 14/ 2004 በሙስሊሞች የተደረገዉን ሰላማዊ ተቃዉሞ ተከትሎ መንግስት “የደህንነት ሰጋት” የሚል ማመካኛን በመፍጠር 28 ሙስሊሞችን አስሮ በጥር 24/2005 ክስ ያቀረበባቸዉ ቢሆንም በታህሳስ 3/2006 አስሩን በነጻ አሰናብቶ በአስራ ስምንቱ ላይ ያቀረበዉን ክስ ዝቅ አድርጓል። መንግስት እነዚህን የሙስሊም ታሳሪዎች በአለማችን ላይ ከሚታወቁ አሽባሪ ድርጅቶች ጋር ግንኙነት አላቸዉ ብሎ በገሃድ ለመፈረጅ መሞከሩም በሪፖርቱ ተገልጿል።

የኢትዮጵያ መንግስት የመናገር-የመደራጀት-የመሰብሰብን መብት የሚተገብሩ ፖለቲከኞችናና ጋዜጠኞችን እንደሚያስር፣ እንደሚያሰቃይ፣ እንደሚያንገላታ፣ የሚገልጸዉ ሪፖርት ከፖለቲከኞች የመድረኩ አንዱአለም አራጌ ብሎም የኦሮሞን ማህበረስብ መብት በዲሞክራሲ ለማስከበር ከሚንቀሳቀሱ የኦሮሞ ተወላጆች በቀለ ገርባና ኦልባና ሌሊሳ ታስረዉ እየተሰቃዩ መሆናቸዉን፤ ተመሳሳይ በሆነ መልኩ ከጋዜጠኞች እስክንድር ነጋ፣ሪዮት አለሙና ሰለሞን ከበደ በእስር ይማቅቃሉ ሲልም ሪፖርቱ ያስረዳል።

መንግስት ነጻ-ፕሬስ እንዲከስም በሚያደርገዉ ከፍተኛ ጫና ጋዜጠኞች የእስርና የስደት ሰለባ መሆናቸዉ ቢታወቅም፤ዳግም መንግስት የአፈና መረቡን በመዘርጋት የኢንተርኔት፣ የሳተላይት-ቴሌቭዥን ስርጭትን፣የማህበራዊ መገናኛ መደረኮችን፣የድረ ገጽ የመረጃ አዉታሮችን በማወክ ህዝቡ ማግኘት የሚገባዉን መረጃ ከማፈኑም ባሻገር፤ የጋዜጠኖች፣ የፖለቲከኞች እና የአክትቪስቶችን ኮምፒዉተር ለመሰለል ህገወጥ የሆነ የኮምፒዉተር ቫይረስን መንግስት እንደሚልክ ሲት ዝን ላብ (citizen lab) የተባለዉን ድርጅትን መረጃ ዋቢ ያደረገዉ የዩናይትድ እስቴትስ አመታዊ የሰብዓዊ መብት ሪፖርት የኢትዮጵያ መንግስት የህዝብ የሆኑ የሬዲዮና የቴሌቭዥን ጣቢያዎችን ሙሉ በሙሉ ተጠቅሞ ለፖለቲካዊ ፕሮፓጋንዳ እየተገለገለባቸዉ መሆኑን ይፋ አድርጓል።

↧
↧

በሳዑዲ አረቢያ የታመቀው የኢትዮጵያውያን ሮሮ ፈንድቶ ዛሬ በሽሚሲ ሁከት ነግሶ ዋለ

$
0
0

* የጅዳ ቆንስል ሃላፊዎች ሆይ ለወገኖቻችሁ ድረሱላቸው!
* ተጽእኖ ፈጣሪዎችም እታድክሙን ፣ ሂዱና እየሆነ ያለውን ተመልከቱ!

ዘገባ ነብዩ ሲራክ ከሳዑዲ አረቢያ

(ፎቶ ፋይል)

(ፎቶ ፋይል)

ሰሞኑን ከጅዳው የሽሜሲ ጊዜያዊ የእስር ማቆያ ውስጥ የሚገኙ በርካታ ኢትዮጵያውያን ለወራት በእስር ተንገላታን ሲሉ የመረረ ሮሯቸውን ገለጹልኝ ። ሮሯቸወ ሰሚ ማጣቱን አምርረው የገለጹልኝ ወገኖች ከእኔ አልፎ ተርፎ ለጀርመን ራዲዮ የዝግጅት ክፍል ሳይቀር ምሬት ሮሯቸውን ማስተላለፋቸውን ገልጸውልኛል።

ዛሬ ረፋድ ላይም በተንቀሳቃሽ ስልኬ ደውለው እጃችሁን ስጡ ተብለው በሰጡ እየደረሰባቸው ያለው መጉላላት በመክበዱ ወደ የሞት ሽረት አድርገው ቁርጡን ለማወቅ እንደሚገደዱና ይህንንም ” ለጅዳ ቆንስል መስሪያ ቤት ሃላፊዎችና ለአለም ድምጻችን አሰማልን !” ሲሉ እያለቀሱ ሃሳባቸውን ሲያስረዱኝ መጭውን ለመገመት አዳጋች አልነበረም።

የግፉአኑ የአደራ ቃል አለብኝና ስልኬን እንደዘጋሁ ወደ ጅዳ ቆንስል ሃላፊዎች ወደ ተጠባባቂው ቆንስል ጀኔራል ሸሪፍ ከይሩ ደወልኩ ። ስልካቸው ይጠራል ግን አያነሱትም! ደጋግሜ ደወልኩ መልስ የለም … ተስፋ ሰንቄ ወደ ሌላኛዋ የቆንስል መስሪያ ቤቱ ሃላፊ ወደ ቆንስል ሙንትሃ ደወልኩበ። እርሳቸውም አያነሱም! ደጋገምኩት ፣ መልስ ግን የለም ! የሚያዝ የሚጨበጥ ማጣት እንዴት ያማል?

ከሰአታት በኋላ እኩለ ቀን ከዚያው ከሽሜሲ ተደውሎለወኝ ስልኩን ሳነሳው የሰው ጫጫታ ፣ እሪታ ፣ አኡኡታና የጥይት ድምጽ ሰማሁ … ደዋዩን ወንድም ምን አዲስ ነገር ተፈጠረ ? አልኩት “መረረን ፣ ድረሱልን አልን ፣ የሚሰማን አጣን ፣ እስር ቤቱን ሰብረን ወጣን !” አለኝ ትንፋሹ ቁርጥ ቁርጥ እያለ መለሰልኝ … ከዚያን ሰአት ጀምሮ እስከ አሁኗ ሰአት ከሽሜሲ የሚደርሰኝ መረጃ ደስ አይልም ! የቆንስል መስሪያ ቤቱ ሰራተኞች በአካባቢው የተገኙ ቢሆንም መፍትሄ ማምጣት ግን የቻሉ አይመስልም።

የጅዳ ቆንስል ሃላፊዎች ሆይ ለመረጃ ቅርብ ሁኑ ! ወገንን ለመደገፍ ትጉ ! የወገኔን የወገናችሁን ክፉ ደግ መረጃ እንዳላቀብል ፣ አታስተላልፍ ከፖለቲካው ጋር እያገናኛችሁ ከመወንጀል እስከ ተራ አሉባልታ የምትሞጅሩኝ የምትሞግቱኝ ተሰሚነት ያላችሁ ተጽእኖ ፈጣሪዎች ሆይ ! አታድክሙን ! ስሙኝ ? እነሆ እየሆነ ያለውን ሂዱና ተመልከቱ ! የምትቆረቆረቆሩት ለወገኖቻችሁ ከሆነ እነሆ ድረሱላቸው።

በቃ ! ሌላ ምን ይባላል ?
ነቢዩ ሲራክ

↧

በምዕራብ ሃረርጌ የታሰሩት ሼህ ሃሰን በእስር ቤት ሕይወታቸው አለፈ

$
0
0
(ፎቶ ፋይል)

(ፎቶ ፋይል)

ድምጻችን ይሰማ እንደዘገበው፦ በኦሮሚያ ክልል በምዕራብ ሃረርጌ በጭሮ ከተማ በሚገኙ ከተለያዩ ወረዳዎች በፖሊስ ተይዘው በጭሮ ከተማ ማረሚያ ቤት ለረጅም ጊዜ ታስረው ለህክምና ወደ ቃሊቲ ማረሚያ ቤት እንዲዘዋወሩ ከተደረጉት ታሳሪዎች መካከል ሼህ ሃሰን በቂ ህክምና ባለማግኘታቸው ሕይወታቸው ማለፉን ምንጮች አስታወቁ፡፡

በጭሮ ከተማ ከተለያዩ ወረዳዎች በጭሮ ከተማ ማረሚያ ቤት ታስረው ባደረባቸው ከፍተ|ኛ ህመም ምክንያት ማረሚያ ቤቱ ከአንድ አመት በፊት ወደ ፌደራል ማረሚያ ቤት ወደሆነው ቃሊቲ ማረሚያ ቤት ሪፈር በመፃፍ ወደ አዲስ አበባ ሄደው እንዲታከሙ ለማድረግ ሞክሮ ነበር፡፤ ሆኖም ታሳሪዎቹ በቃሊቲ ማረሚያ ቤት በዞን 3 ታስረው የሚገኙ ሲሆን ምንም የረባ ህክምና ሳያገኙ በከፍተኛ ህመም እየተሰቃዩ እንደሚገኙ ምንጮች አስታውቀዋል፤፤

ከምዕራብ ሃረርጌ ጭሮ ከተማ ማረሚያ ቤት ወደ ቃሊቲ ማረሚያ ቤት ከአመት በፊት የተዘዋወሩት ታሳሪዎቹ ስም ዝርዝር እንደሚከተለው ይቀርባል

1.መሐመድ ሐሰን አሊዩ በምዕራብ ሀርርጌ ዞን ጭሮ ከተማ ደባቢስቶ ወረዳ ቡሌ ኢሉ ቀበሌ

2.መሃመድ አህመድ በምዕራብ ሀርርጌ ዞን ጭሮ ከተማ ደባቢስቶ ወረዳ ቡሌ ኢሉ ቀበሌ

3.ሼህ ሀሰን በምዕራብ ሀረርጌ ዳሮ ለቦ ወረዳ ገለሞተራ ቀበሌ

4.ከተማ ጸጋዬ መገናኛው በምዕራብ ሃረርጌ መቻሬ ወይም ገመቺስ ወረዳ ሽሬ ቡሉ ቀበሌ

5.ከተማ ለማ ኢሾ በምዕራብ ሃረርጌ መቻሬ ወይም ገመቺስ ሽሬ ቡሉ ቀበሌ

6.ዘውዱ ታሪኩ እንደሻው በምዕራብ ሃረርጌ ዳርጌ ሳውሮ ወረዳ ቀበሌ 34 ነዋሪ የነበሩ መሆናቸው ታውቋል፡፡

ከላይ ከተዘረዘሩት በቃሊቲ ማረሚያ ቤት በዞን 3 ታስረው ከሚገኙት ታሳሪዎች መካከል በምዕራብ ሃረርጌ የጭሮ ከተማ የደባቢስቶ ወረዳ ቡሌ ኢሉ ቀበሌ ነዋሪ የነበሩት ሼህ ሃሰን በማረሚያ ቤቱ በቂ ህክምና እንዳያገኙ በመደረጋቸው በየካቲት 15/2006 ሂወታቸው ማለፉን የማረሚያ ቤቱ ምንጮች አስታውቀዋል፡፡

ሼህ ሃሰን ከጭሮ ከተማ ማረሚያ ቤት በቂ ህክምና እንዲያገኙ በሚል አብረዋቸው ከታሰሩ ሌሎች ታሳሪዎች ጋር ወደ አዲስ አበባ ቃሊቲ ማረሚያ ቤት ቢዘዋወሩም ማረሚያ ቤቱ ተገቢ እና በቂ ህክምና እንዳያገኙ በማድረጉ ከዚህ አለም በሞት ሊለዩ እንደቻሉ ታውቋል፡፡ የሼህ ሀሰን ቤተሰቦችም ሊያገኟቸው አለመቻላቸውን የማረሚያ ቤቱ ምንጮች ገልፀዋል፡፡

በተመሳሳይም ሁኔታ ሌላኛው በምዕራብ ሀርርጌ ዞን ጭሮ ከተማ ደባቢስቶ ወረዳ ቡሌ ኢሉ ቀበሌ ነዋሪ የነበረው እና የዞን 3 ታሳሪ የሆነው .መሐመድ ሐሰን አሊዩ በቂ ህክምና ባለማግኘቱ በማረሚያ ቤቱ ውስጥ በሞት አፋፍ ላይ እንደሚገኝ ምንጮች አስታውቀዋል፡፡

በኢትዬጲያ በሚገኙ ማረሚያ ቤቶች ታስረው የሚገኙ ዜጎች ከጊዜ ወደ ጊዜ በህክምና እጦት ምክንያት ሂወታቸው በስቃይ የሚያልፉ ታሳሪዎች ቁጥር እየጨመረ መምጣቱ እየተሰማ ሲሆን የማረሚያ ቤቶቹ አስተዳደሮች ለሰው ልጅ ሂወት ክብር በመንፈግ ይህን ችግር ከመቅረፍ ይልቅ የፖለቲካ መቅጫ ዘዴ አድርገው መቀጠላቸው ታውቋል፡፡

ከዚህ ቀደም በቂሊንጦ ማረሚያ ቤትም ወረርሽኝ ገብቶ ጋዜጠኛ ዩሱፍ ጌታቸውን ጨምሮ በርካታ የማረሚያ ቤቱ ታሳሪዎች ለህመም ተጋልጠው እንደነበር ይታወሳል፡፤ በማረሚያ ቤቱ ባለው የንፅህና ጉድለት እና መጥፎ ሽታም ኮሚቴዎቻችንንም ጨምሮ ለከፍተኛ የሳይነስ እና ተዛማጅ በሽታዎች ተጋላጭ እንዲሆኑ እንዳደረጋቸው ይታወቃል፡፡

↧

በዳላስ የምትነዳው መኪና ከባቡር ጋር ተጋጭቶ ሕይወቷ ያለፈው ወጣት ኢትዮጵያዊት ናት ተባለ

$
0
0

melat mamo 11 (ዘ-ሐበሻ) የዳላስ/ቴክሳስ ሚዲያዎች ትናንት ቅዳሜ በፌር ፓርክ አካባቢ የአንድ ሰው ሕይወት መኪና ከባቡር ጋር ተጋጭቶ መጥፋቱን ዘግበው ነበር። የዘ-ሐበሻ የዳላስ ምንጮች እንደጠቆሙት ከባቡሩ ጋር በመኪና ተጋጭታ ሕይወቷ ያለፈው ኢትዮጵያዊት ናት።

የዳላስ ፖሊስ ትናንት ማምሻውን በሰጠው መግለጫው ባቡሩ መንገዱን በሚያቋርጥበት ወቅት መብራቶች እና ደውሎች እየተሰሙ የነበሩ ቢሆንም መኪናው ውስጥ የነበረ ሹፌር ይህን ደውልና መብራት ባለማስተዋል በሚያቋርጥበት ወቅት አደጋው ደርሷል። ከዳላስ በደረሰን መረጃ መሠረት በዚህ አደጋ ሕይወቷ ያለፈው ኢትዮጵያዊት ስትሆን ስሟም ሜላት ማሞ እንደሚሰኝ ከፎቶ ግራፏ ጋር የደረሰን መረጃ ያመለክታል።

በዳላስ ፖሊስ መረጃ መሠረት የተሳፋሪዋ ባቡሩና መኪናዋ በፈጠሩት ግጭት የተሳፋሪዋ ሕይወት ወዲያውኑ አልፏል። ይህን ተከትሎ በዳላስ ያሉ ኢትዮጵያውያን በወገናቸው ሕልፈት የተሰማቸውን ሃዘን በመግለጽ ላይ ይገኛሉ።

እንደፖሊስ መረጃ ባቡሩ 24 ሰዎችን ይዞ ይጓዝ የነበረ ሲሆን ማንም ሰው ወደ ሆስፒታል ባይወሰድም 4 ሰዎች ጉዳት ደርሶብናል ብለዋል።

ሜላት ሃገሯን እና ወገኗን ወዳድ እንደነበረች የሚያውቋት የሚመሰክሩ ሲሆን በቅርቡ በሳዑዲ አረቢያ በወገኖቻችን ላይ የደረሰን ጥቃት ተከትሎ በዳላስ በተደረገው የተቃውሞ ሰልፍ ላይ ከኢትዮጵያውያን ጋር በመሆን ድምጿን ስታሰማ ነበር። (ፎቶው ከታች አያይዘነዋል)።

ፈጣሪ ነብሷን በገነት እንዲያኖረው ዘ-ሐበሻ በዚህ አጋጣሚ ሃዘኗን ትገልጻለች።
melat mamo
melat mamo dallas 2

↧

“ኢትዮጵያ በተደራጀ ምዝበራ እየደማች ነው”–ዶ/ር አክሎግ ቢራራ (ሊያደምጡት የሚገባ ቃለምልልስ)

$
0
0

“ኢትዮጵያ በተደራጀ ምዝበራ እየደማች ነው፤ ይሔ ውጭ ውጭውን የሚታየው ህንጻ በአገሪቱ ላይ የተንሰራፋው ድህነት ግርዶሽ ነው”
- ዶ/ር አክሎግ ቢራራ
aklog ዶ/ር አክሎግ ቢራራ የቀድሞ የዓለም ባንክ የኢኮኖሚ አማካሪና ተመራማሪ በህብር ሬዲዮ አራተኛ ዓመት በዓል ላይ በመገኘት ካቀረቡት ጥናታዊ ሪፖርት የተወሰደ

የህብር ሬዲዮ 4ተኛ ዓመት በዓል ላይ ባለፈው ረቡዕ የካቲት 26 /2014 በቬጋስ በመገኘት ዶ/ር አክሎግ ቢራራ በልማት ስም ግርዶሽ የሚለውን ጥናታቸውን ለበዓሉ ተሳታፊዎች አቅርበዋል። ከበዓሉ ማግስት ለዶ/ር አክሎግ የተለያዩ መሰረታዊ ጥያቄዎችን ሕብር ራድዮ አቅርባ መልሰዋል። ይከታተሉት።

↧
↧

730 ቀናት ለሃይማኖት ነፃነት (730 Days For Religious Freedom) ዘጋቢ ፊልም ይፋ ሆነ

$
0
0

የኢትዮጵያ ሙስሊሞች እንቅስቃሴ የተጀመረበትን ሁለተኛ ዓመት ለማሰብ ድምጻችን ይሰማ “730 ቀናት ለሃይማኖት ነፃነት (730 Days For Religious Freedom)” የሚል ዘጋቢ ፊልም አዘጋጀ። 56 ደቂቃ ከ34 ሰከንድ የሚፈጀው ይኸው ፊልም ለዘ-ሐበሻ አንባቢዎች ግንዛቤ ይረዳ ዘንድ አስተናግደነዋል – እነሆ፦

730 ቀናት ለሃይማኖት ነፃነት (730 Days For Religious Freedom) ዘጋቢ ፊልም ይፋ ሆነ

↧

Hiber Radio: ሱዳን በአገሯ የኢትዮጵያ አማጺያንን እያሰለጠነች መሆኑ ተገለጸ

$
0
0

የህብር ሬዲዮ የካቲት 23 ቀን 2006 ፕሮግራም
እንኳን ለአድዋ ድል 118ኛው በዓል አደረሳችሁ!!

ጋዜጠኛ ሃብታሙ አሰፋ

ጋዜጠኛ ሃብታሙ አሰፋ

<... ...>>

ዶ/ር አክሎግ ቢራራ የቀድሞው የዓለም ባንክ የኢኮኖሚ አማካሪ ለህብር ሬዲዮ ከሰጡት ቃለ ምልልስ(ሙሉውን ያዳምጡ)

<... ...>

አቶ ስዩም መንገሻ የአንድነት ዋና ጸሐፊ የአድዋን 118ኛ በዓልን በአዲስ አበባ ስላከበሩበት ሁኔታ ተጠይቀው ከሰጡት ምላሽ(ሙሉውን ያዳምጡት)

>

አቶ ጴጥሮስ አሸናፊ ረዳት አብራሪው እንዲፈታ ጥረት የሚያደርገው ግብረ ሀይል አባል ለህብር ከሰጡት ቃለ ምልልስ የተወሰደ

የህብር ሬዲዮ አራተኛ ዓመት በዓል ልዩ ሪፖርት

ሌሎችም ዝግጅቶች

ዜናዎቻችን

- ሙስና ኢትዮጵያን እያጠፋት መሆኑን የቀድሞው የዓለም ባንክ የኢኮኖሚ አማካሪ ገለጹ

- ሱዳን በአገሯ የኢትዮጵያ አማጺያንን እያሰለጠነች መሆኑ ተገለጸ

- ኢትዮጵያውያን ግፍ በዛብን ብለው የሳውዲን እስር ቤት ሰብረው ወጡ

* ጩኸትና የጥይት ተኩስ ተሰምቷል

- የአድዋ ድልን መዘከር ብቻ ሳይሆን በአንድ ላይ ቆመው ለመብታቸው እንዲታገሉ ጥሪ ቀረበ

- ተቃዋሚዎችም እንዲተባበሩ ተጠይቋል

- ኩዌት ኢትዮጵአውያን የጉልበት ሰራተኞችን አልቀበልም አለች

- ረ/አብራሪ ሀይለመድህንን የስዊዝ መንግስት ጥገኝነት እንዲሰጠው የሚጠይቅ ፊርማ መሰብሰብ ተጀመረ

- የመጀመሪያው ድሪም ላይነር አብራሪና የአየር መንገዱ ም/የስራ ሀላፊ በፈቃዳቸው ለቀቁ ተባለ

- አንድነት በባህር ዳር ያደረኩትን ተቃውሞ አዲስ አበባን ጨምሮ በ12 የአገሪቱ ከተሞች ይቀጥላል አለ

ሌሎችም ዜናዎች አሉ

↧

የተምቤን ስብሰባችን ጉድ አደረገን (አብርሃ ደስታ)

$
0
0

ህወሓቶች በተለያየ አከባቢ የሚገኙ ወጣቶች ሰብስበው እያነጋገሩ ነው። የስብሰባው ዓላማም “በተቃዋሚዎች እንዳትሸወዱ፣ ከህወሓት ዉጭ ሌላ አማራጭ የላችሁም፣ ስራ እንሰጣችኋለን፣ በተቃዋሚዎች ስብሰባ እንዳትሳተፉ …” ወዘተ እያሉ ወጣቶቹን ለማስጠንቀቅ ነው።

ህወሓቶች ከልክ በላይ ፈርተዋል። ዓላማቸው ሁሉ ህዝብ በዓረና ስብሰባ ላይ እንዳይሳተፍ ማድረግ ነው። ለምን ይህን ያህል ፈሩ? የተምቤን ስብሰባችን ነው ጉድ ያደረገን። በተምቤን ዓብይዓዲ ስብሰባ በጠራንበት ግዜ ህወሓቶች የተከተሉት ስትራተጂ መጀመርያ ህዝብ ወደ ስብሰባ እንዳይገባ መከልከል፣ በድፍረት በስብሰባው ለመሳተፍ ከገባ ግን የህወሓት ካድሬዎችን በመላክና “ጠንካራ” ጥያቄዎችን በማንሳት የዓረና መሪዎችን ህዝብ ፊት ማዋረድ፣ ካድሬዎቹ የመከራከርና የመጠየቅ ዕድል ከተነፈጉ ደግሞ “ዴሞክራሲያዊ አይደሉም” በማለት በህዝብ ፊት ማጋለጥ የሚል ነበር።

አብርሃ ደስታ

አብርሃ ደስታ


ህዝብ በስብሰባው እንዳይሳተፍ የነበረ ዕቅድ አልተሳካም። ምክንያቱም ህዝቡ የካሬዎች ማስፈራራት ሳይበግረው ገባ። ካድሬዎችም ለመከራከርና ለመጠየቅ ገቡ። ጠየቁ፤ ተከራከሩ። እኛም በቂ መልስ ሰጠን። ተሳታፊም ገመገመን። በስብሰባው የተሳተፉ ካድሬዎች ሳይቀሩ በኛ ሐሳብ ተስማሙ። በህወሓት ስብሰባዎችም የዓረና አመራር አባላት ያነሱት ሐሳብ ተነሳ። እንዲረብሹን የተላኩ ካድሬዎች ጭራሽ የኛ ተወካዮች ሁነው በራሳቸው (በህወሓት) ስብሰባ የዓረና አጀንዳ እያነሱ መከራከር ጀመሩ። ህወሓቶች በዓረና ስብሰባ የተሳተፉ የህወሓት አባላት በሙሉ ዓረና ሁነዋል ብለው ደመደሙ። ከዛ በኋላ ማንም የህወሓት አባል ዓረና በሚጠራው ስብሰባ እንዳይሳተፍ ትእዛዝ ተሰጠ። (በየዞኑ ይካሄድ በነበረ የህወሓት ካድሬዎች ስብሰባ የተምቤን ካድሬዎች ጤነኞች አይደሉም በሚል ምክንያት ከሌሎች ጋር ሳይቀላቀሉ ለብቻቸው እንዲሰበሰቡ ተደርጓል)።

ከተምቤን ስብሰባ በኋላ ዓረና ህዝብ ሰብስቦ ማነጋገር አልቻለም። የሽረ፣ ዓዲግራትና ሑመራ ተረብሿል። አሁን ህወሓቶች እየተከተሉት ያለ ስትራተጂ ህዝብ በዓረና ስብሰባ እንዳይገኝ መከልከል ብቻ ነው። ምክንያት: በዓረና ስብሰባ የተሳተፈ ሰው (የህወሓት አባል ጭምር) ዓረና የመሆን ዕድሉ ከፍተኛ ነው የሚል ነው።

አሁን በብዙ አከባቢዎች እየተደረገ ያለው ጥረትም ህዝብ ሌላ አማራጭ የፖለቲካ ድርጅት ሐሳብ እንዳይሰማ በራሳቸው ፕሮፓጋንዳ ማደንቆር ነው። ዓረና ህዝብ እንዳይሰበስብ በመከልከል ራሳቸው ስብሰባ እየጠሩ በዓረና ስብሰባ እንዳይሳተፍ ያስጠነቅቁታል። ህዝብ ግን ለውጥ ይፈልጋል፣ ተነሳስቷል።

የትግራይ ህዝብ ለምንድነው የራሱ የፖለቲካ አስተሳሰብ እንዲያዳብር የማይፈቀድለት? ለምንድነው በህወሓቶች ትእዛዝ እንዲያስብ፣ እንዲጓዝ የተፈረደበት? የትግራይ እናት የህወሓት ሰዎች ወልዳ መክናለች ያለ ማነው? የትግራይ ህዝብ የፈለገውን የመከተል መብቱ የተነፈገው ብዙ መስዋእትነት ስለከፈለ ነው? በነፃነት ለመኖር መስዋእት መክፈል አያስፈልግም ማለት ነው? እልህ አስጨራሽ ትግል አድርጎ፣ ብዙ መስዋእትነት የከፈለ ህዝብ ለምን በነፃነት እንዳያስብ ታፈነ? ወጣቶችን በመሰብሰብ ህወሓቶች ከሚጓዙበት መንገድ ዉጭ ሌላ አቅጣጫ መከተል ስህተት እንደሆነ መስበክ ለወጣቶቹ ያለንን ንቀት አያሳይም? ወጣቶችኮ የራሳቸው መንገድ አላቸው። ለምን ነፃ እንዲሆኑ አይፈቀድላቸውም?

አዎ! በዓረና ስብሰባ የተሳተፈ ሁሉ ዓረና እንደማደርገው አልጠራጠርም፣ የህወሓት አባላትም ጭምር። ያለኝ ዕቅድ በዓረና ስብሰባ የተሳተፈ ሁሉ ዓረና ማድረግ ነው፤ እንደ ህወሓት በጠብመንጃ በማስፈራራት ወይ ገንዘብና ስልጣን በመስጠት አይደለም። በሐሳብ በማሳመንና የለውጥ አስፈላጊነት በማስረዳት እንዲሁም ዴሞክራሲያዊ ስርዓትን የመገንባት ተልእኮአችን በመጠቆም እንጂ።

ወጣቶች ሆይ! በስብሰባ እንዳትሳተፉ የሚደረግ ማንኛውም ትእዛዝ አትቀበሉ። ምክንያቱም በየትኛውም ስብሰባ የመሳተፍ መብት አላቹ። በስብሰባ ለመሳተፍና ላለመሳተፍ የሚወስንላቹ ህወሓት ሳይሆን እናንተ ናችሁ። ምክንያቱም በህይወታቹ ላይ ተፅዕኖ ላለው ጉዳይ የመወሰን ነፃነቱ ሊኖራቹ ይገባል። ህወሓት ከናንተ በላይ ስለናንተ አያውቅም። በለውጥ ሂደቱ ተሳታፊ ሁኑ። ህልውናችሁን አረጋግጡ። ህወሓት እየሰራው ያለው ተግባር በራሱ ዓፈና ነው። ጭቆና ነው። ፀረ ዓፈና ተነሱ። ጭቆናን አስወገድን ነፃነታችንን እናስመልስ።

እዛው በነፃነት ሥፍራው እንገናኝ። እጠብቃችኋለሁ።

It is so!!!

↧

Sport: ማንቸስተር ዩናይትድ ከድጡ ወደ ማጡ

$
0
0

man 2
ከይርጋ አበበ

የማንቸስተር ዩናይትድ ስታዲየም ከአፍ እስከ ገደፉ ክለባቸውን በሚያፈቅሩ እንግሊዛውያን ተሞልቷል። ከቁጥራቸው በተጨማሪም ለሰከንድ በማይቋረጥ ዝማሬያቸው ስታዲየሙን ልዩ ድባብ ሰጥተውታል። በዴቪድ ሞይስ የሚሠለጥነው ማንቸስተር ዩናይትድ የምዕራብ ለንደኑን ፉልሃምን እያስተናገደ ነው። ከእነዚህ የኦልድትራፎርድ አድማቂዎች መካከል አንዱ የቀድሞው የክለቡ አሠልጣኝ ሰር አሌክስ ፈርጉሰን ይገኙበታል። ያች እለት ለኦልድትራፎርዱ ክለብ ደጋፊዎች ልዩ ነበረች። ምክንያታቸው ደግሞ በ1968 ሙኒክ ላይ በደረሰው የአውሮፕላን አደጋ የሞቱትን የቀድሞ ኮከብ ሰማዕቶቻቸውን የሚዘክሩበት እለት መሆኑ ነው። የሰር አሌክስ ፈርጉሰን በእለቱ በስታዲየም ተገኝተው ጨዋታውን መከታተላቸው ግን ከእዚያ ክስተት ጋር ግንኙነት የለውም፤ ምንጊዜም እንደሚያደርጉት ክለቡ ሲጫወት ስታዲየም እየተገኙ መከታተል ስለሚወዱ ነበር።

ጨዋታው ተጀመረ። ስቲቭ ሲድዌል የተባለ የፉልሃም አማካይ እንግዳውን ክለብ ቀዳሚ ያደረገች ግብ ሲያስቆጥር ቀይ ፎጣ አንገታቸው ላይ አስረው ክለባቸውን የሚያበረታቱ የማንቸስተር ዩናይትድ ደጋፊዎችን አንገት ማስደፋት ጀመረ። ማንቸስተር ዩናይትድ ከተመሪነት ተነስቶ በእንግዳው መረብ ላይ ሮቢን ቫን ፐርሲና ማይከል ካሪክ ባስቆጠሯ ቸው ሁለት ግቦች መምራት ሲጀምር ሞራላቸው ወድቆ የነበረው የክለቡ ደጋፊዎች ትልቅ ተስፋ ሰንቀው መሳቅ ጀመሩ። ሰር አሌክስ ፈርጉሰንም በቀድሞ ክለባቸው ድል አድራጊነት ተማምነው ደስታቸውን ከጎናቸው ለተቀመጡት ጓደኛቸው ያጋሯቸው ጀመር። ዳሩ ግን መደበኛው የጨዋታ ክፍለ ጊዜ ተጠናቅቆ የእለቱ ዳኛ የጨመሩት አራት ደቂቃ ሁሉ ሊጠናቀቅ ሽርፍራፊ ሰከንዶች ሲቀሩት ተቀይሮ የገባው የፉልሃሙ የፊት መስመር ተሰላፊ ዳረን ቤንት የሰር አሌክስ ፈርጉሰንንና የዴቪድ ሞይስን አንገት ያስደፋች፤ የክለቡን ደጋፊዎችም አንጀት ያሳረረች ግብ በማስቆጠር ማንቸስተር ዩናይትድ ነጥብ እንዲጥል አስገደደው።

ይህ የሆነው ከአራት ሳምንታት በፊት ነበር። ከዚያች እለት ጀምሮ ክለቡ ካደረጋቸው ተከታታይ ሦስት ጨዋታዎች በማሸነፍ ከገባበት የውጤት ቀውስ ያገገመ ቢመስለም ከሰሞኑ በአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ የገጠመው ውጤት አስደንጋጭ ተብሏል። በአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ሁለተኛው ዙር (ጥሎ ማለፍ) ተሳታፊ ከሆኑት ክለቦች መካከል አንዱ የሆነው ማንቸስተር ዩናይትድ ከትናንት በስቲያ ማክሰኞ ምሽት ወደ አቴንስ ተጉዞ የግሪኩን ኦሎምፒያኮስን ገጥሞ ነበር። በዚህ ጨዋታ ማንቸስተር ዩናይትድ በቀላሉ ባያሸንፍ እንኳ ለመልሱ ጨዋታ የሚጠቅመውን ውጤት ይዞ ይመለሳል ተብሎ ተጠብቆ ነበር። ዳሩ ግን ባለሜዳዎቹ ሁለት ለባዶ አሸንፈው የዴቪድ ሞይስንም ሆነ የክለባቸውን የቁልቁለት ጉዞ አፋጠኑባቸው።

ከጨዋታው በኋላ አስተያየቱን የሰጠው የቀድሞው የማንቸስተር ዩናይትድ አምበል ሮይ ኪን «ለማንቸስተር ዩናይትድ መጫወት ምን ማለት እንደሆነ ያልተረዱ » ሲል ነበር በቀድሞ ክለቡ ተጫዋቾች ላይ የተሳለቀው። ማንቸስተር ዩናይትድ በእለቱ ሁለቱን አጥቂዎች (ዋይኒ ሩኒንና ሮቢን ቫንፐርሲን) በቋሚነት ቢያሰልፍም በ90ደቂቃ የሜዳ ላይ ቆይታ የተጋጣሚውን ግብ ጠባቂ መፈተን የቻለው አንድ ጊዜ ብቻ ነበር።

አሁን ሁኔታዎች ሁሉ ለዴቪድ ሞይስ ከባድ እየሆኑባቸው ነው። ምክንያቱ ደግሞ ክለቡ ከሚወዳደርባቸው ሦሰት ውድድሮች ( ካፒታል ዋን፣ ኤፍ ኤ ካፕ፣ፕሪሚየር ሊግ) ዋንጫዎች ቀስ በቀስ ከተፎካካሪነት ውጪ ሆኗል። ክለቡ ዋንጫ አገኝበታለሁ ብሎ ተስፋ ያደረገው ደግሞ የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ዋንጫ ነበር። ከወዲሁ በጥሎ ማለፉ የመጀመሪያ ጨዋታ ሁለት ለባዶ መሸነፉ ደግሞ ዋንጫ የማግኘት ተስፋውን አጨልሞበታል።

እንደዚህ አይነት የውጤት ማጣት ቀውስ ውስጥ የገቡት ዴቪድ ሞይስ በኦልድትራፎርድ የሚኖራቸው ቆይታ «የዛፍ ላይ እንቅልፍ ሆኗል፤» ቢባሉም እንደ አርሴን ቬንገር አይነት አሰልጣኝ ግን ለዴቪድ ሞይስ ጠበቃ መቆም የፈለጉ ይመስላሉ። ቬንገር ምክንያት አላቸው። የቀድሞው የዴቪድ ሞይስ ክለብ ኤቨርተን በ2006 የውድድር ዘመን ፕሪሚየር ሊጉ ተጀምሮ ስምንት ጨዋታዎች ቢያልፉም ሃያኛ ደረጃን ማለፍ ተስኖት በደረጃው ግርጌ ላይ ለረጅም ጊዜ ተኝቶ ቆይቶ ነበር። ሆኖም በውድድር ዓመቱ መጨረሻ ኤቨርተን እንደ ቶተንሃም፣ ኒውካስትልና ማንቸስተር ሲቲ አይነት ክለቦችን ቀድሞ አምስተኛ ደረጃን ይዞ አጠናቀቀ። ቬንገር ይህ ታሪክ ሊደገም ባይችል እንኳ ዴቪድ ሞይስ ጊዜ ሊሰጣቸው ይገባል ባይ ናቸው።

በርካቶች ግን በቬንገር ሃሳብ አይስማሙም። ለሃሳባቸው ማጠናከሪያ የሚያቀርቡት ደግሞ ማንቸስተር ዩናይትድ በዴቪድ ሞይስ አሰልጣኝነት እየተመራ ባለፉት ሰባት ወራት ያስመዘገበውን ደካማ ውጤት በመጥቀስ ነው። ከእነዚህም መካከል ክለቡ በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ከ1972 የውድድር ዓመት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ በሜዳው በኒውካስትል ዩናይትድ መሸነፉ፣ ከ1978 በኋላ ዌስትብሮሚች ኦልድትራፎርድ ላይ አግኝቶት የማያውቀውን ሙሉ ሦስት ነጥብ በዚህ ዓመት ማሳካቱ፣ የደቡብ ዌልሱ ስዋንሲ ሲቲ ኦልድትራፎርድ ላይ በታሪኩ የመጀመሪያውን ሙሉ ሦስት ነጥብ ማሳካት የቻለውም በዚሁ የውድድር ዓመት በዴቪድ ሞይስ አሰልጣኝነት ዘመን ነው። በአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ማንቸስተር ዩናይትድ በታሪኩ በግሪኩ ኦሎምፒያኮስ ሲሸነፍ የመጀመሪያ ጊዜ ሲሆን፤ ስቶክ ሲቲና ኤቨርተንም ቢሆኑ ከረጅም ዘመናት ቆይታ በኋላ በማንቸስተር ዩናይትድ ሜዳ ሦስት ነጥበ ማግኘት የቻሉት በዚህ የውድድር ዓመት ነው። በተለይ ስቶክ ሲቲ በሰር አሌክስ ፈርጉሰን አሰልጣኝነት ዘመን ኦልድትራፎርድ ላይ ማንቸስተር ዩናይትድን አሸንፎት አያውቅም ነበር። እንዲሁም ክለቡ በፕሪሚየር ሊጉ በተከታታይ ሦስት ጨዋታዎችን ሲሸነፍ የዘንድሮው ከ13ዓመታት በኋላ የመጀመሪያው ነው። ይህንን ሁሉ የተመለከቱ የክለቡ ደጋፊዎችና የስፖርት ተንታኞች «የማንቸስተር ዩናይትድ ጉዞ የቁልቁለት ነው» እያሉ መናገራቸውን ተያይዘውታል።

↧
↧

የፈራ ይመለስ! (ከተመስገን ደሳለኝ)

$
0
0

በ2004 ዓ.ም የካቲት 23 ቀን በታተመችው ‹‹ፍትሕ›› ጋዜጣ ላይ፣ ‹‹የፈራ ይመለስ!›› በሚል ተመሳሳይ ርዕስ፣ ከሰላማዊ አብዮት ውጪ አማራጭ ካለመኖሩም ባለፈ፣ ኢህአዴግ ቢያንስ ሕገ-መንግስታዊ ጥበቃ ላላቸው ሕዝባዊ ጥያቄዎች ምላሽ የመስጠት አቅምም ፍላጎትም እንደሌለውለመሞገት ሞክሬ ነበር፡፡ ግና፣ አገዛዙ ለእንዲህ ያሉ ግዴታዎች የተዘጋጀ ባለመሆኑ ከማድመጥ-መዳ–መጥን፤ ከመመከር-መከራን፤ ከማሰብ-ቃሊቲ መሰብሰብን፤ ከመሻሻል-ከሀገር ማሸሽን፤ ከማመን-መርገጥን… በመምረጡ፤ ዛሬም ድረስ ነፃነት ናፋቂው ዘመነኛ ትውልድ፣ በፀጥታ አርምሞ ወደተዋጡት አደባባዮች ከማማተር ያለፈ አማራጭ እንዳያገኝ ገፊ-ምክንያት ሆኖ ቀጥሏል፡፡ ያንን ጽሑፉም ከዓመት ከስድስት ወር በላይ ፍርድ ቤት ከምመላለስባቸው ክሶች የአንዱ መወንጀያ አድርጎ በተከበረችዋ ፍትሕ እየተሳለቀባት ነው፡፡ በርግጥ ጉዳዩ ገና እልባት ያላገኘ በመሆኑ፣ በዚህ ተጠየቅ አናነሳውም፡፡
ያ ጽሑፍ የታተመባት ‹‹ፍትሕ›› ጋዜጣ የስርዓቱ ቅጥ ያጣ አፈና ሰለባ የመሆኗን ጉዳይ ግን ሁሌም ስናወሳው እንኖራለን፤ ምክንያቱም የ‹‹ቅድመ-ምርመራ›› (ሳንሱር) ግብአተ-መሬት በግላጭ በሕገ-መንግስቱ ሳይቀር ከታወጀ ሃያ ዓመት ባስቆጠረበት ኢህአዴጋዊ ዘመን የተፈፀመ ታላቅ መብት ረገጣ ነውና፤ ያውም ተራ የወሮበሎች ረገጣ መሆኑን ፍንትው አድርጎ የሚያሳይ፡፡ በመንግስታዊው ብርሃንና ሰላም ማተሚያ ቤት ለዚሁ ሕገ-ወጥ ተግባር አድፍጠው እንዲጠብቁ የተመደቡ ‹ግልገል› ካድሬዎች ጋዜጣዋ የምትታተምበትን ሐሙስ ቀንን በዝምታ አሳልፈው ነገር ግን ድንገት በዕለተ አርብ ማለዳ ‹‹ይህንን ዜና ማውጣት አትችሉም! ቆርጣችሁ አውጡ›› ማለታቸው ነው፤ ምን ዋጋ አለው ትዕዛዛቸው ተቀባይነት ባለማግኘቱ፣ በመቶ ሺህ የሚቆጠር ገንዘብ ውጪ የተደረገበትን፣ 30 ሺህ የጋዜጣዋ ህትመት እንዲቃጠል በፍርድ ቤቱ አማካኝነት በጭካኔ በየኑ፤ ‹‹ፍትሕ››ንም በሕገ-ወጥ መንገድ ዳግም እንዳትታተም አገዱ፤ ይህ ሁሉ ከሆነ እነሆ ሃያ ወራት ተቆጥሯል፡፡ ግና፣ የተከፈለው ሁሉ ስለነገ የተሻለች ኢትዮጵያ ሲባል ነውና ባለፈ ጉዳይ ማለቃቀሱን እዚሁ ገታ አድርገን፣ ኩነቱንም ከነጋዴነት ለተሻገሩ ታሪክ ጸሐፊዎች ትተን፣ በአዲስ መስመር ወደ አጀንዳችን እንለፍ፡፡

የፈራ ይመለስ!
አዎ፣ ይመለስ!! ፍርሃቱን ‹‹አሜን›› ብሎ ተቀብሎ ለመመለስ ከወሰነ በመረጠው የጭቆና ቀንበር እየተቀጠቀጠ ማደር መብቱ ነው፤ ግና፣ አንዳንድ ፈሪዎች፣ አንዳንድ መሀል ሰፋሪዎች በስመ ‹‹ጸሐፊነት›› ጥያቄውን በማጣጣል ለውጡን ለማራዘም (ለማደናቀፍ) የሚያደርጉት ሙከራ ከንቱ እንደሆነ በቅድሚያ ላስገነዝብ እወዳለሁ፡፡ ደግሞም እነኚህ የጭቆና ዘመን አራዛሚዎች እያገለገሉት ያለው ስርዓት የሚያከፋፍለው ብሔራዊ ዳቦ እየተመናመነ መምጣቱን፣ ገዥዎቹ ራሳቸው የፓርቲያቸው ችግር (7 ሚሊዮን የሚደርሱ ካድሬዎችን ከማግበስበሱ አኳያ) ‹‹የጥቅመኞች መብዛት›› እንደሆነ በይፋ አምነው ከተቀበሉት ጋር ስንገምደው የነገ ቀናቸው ‹‹ከኢህአዴግ ጋር ብሩህ›› እንዳልሆነ እግረ መንገዴንም ልጠቁማቸው እፈልጋለሁ፡፡ በአንፃሩ እነዚያ ሀገሪቷን እያሰመጠ ያለውን የመከራ ረግረግ ተረድተው አብዮቱን ተስፋ ያደረጉ ጎበዛዝት እና ወይዛዝርት ደግሞ ይበልጥ እንዲነቁ፣ ይበልጥ እንዲበረቱ… የጊዜውን መቃረብ ላስታውሳቸው እወዳለሁ፡፡ ምክንያቱም በቁጣ አደባባይ ለመውጣት እንቅፋት የሆነው ብሔራዊ ፍርሃት ይሰበር ዘንድ ለመስበክ፣ የዛሬይቱ ኢትዮጵያ በነፃነቷ ትበጽህ ዘንድ ካስረገጠው ከዚህ መቶ አስራ ስምንተኛው የዐድዋ ድል ዋዜማ የበለጠ ምቹ ጊዜ የለምና (ይህ ድል በነፃነት የሚያምን የሰው ልጅ ሁሉ፣ ያለቀለም ልዩነት ሊዘክረው የሚገባ ስለመሆኑ ለእነርሱም ጭምር መመስክር ግዴታ ይመስለኛል)
እንዲህ በጽሑፍ ሲገለፅ በእጅጉ የሚቀለው የዐድዋ ገድል፣ እልፍ አእላፍ የሀገሬ ሰዎች መተኪያ አልባ ህይወታቸውን የገበሩበት በመሆኑ፣ በየዓመቱ ደግመን ደጋግመን የመዘከርና አደራውን የመቀበል ታሪካዊ ግዴታ ውስጥ ጥሎን ማለፉ እውነት ነው፡፡ ‹‹የተሰጠኝ ህይወት ዛሬ በነፃነት፣ ሰው ተከፍሎበታል ከደምና ከአጥንት›› እንድትል እጅጋየሁ ሽባባው (ጂጂ)፤ እኒያ ሰማዕታት ከዳር እስከዳር ነቅለው ‹‹…ሀገር የሞተ እንደሁ ወዴት ይደረሳል?›› በሚል መታመን ተቀስቅሰው፣ ባሕር አቋርጦ፣ አድማስ ተሻግሮ የመጣውን ወራሪ ሀፍረት አልብሰው፣ ሀፍረት አስታጥቀው፣ ሀፍረት አጉርሰው… የመመለሳቸው ብርታት ባለዕዳዎች መሆናችንን ዘመን ሊሽረው አይችልም፡፡ ያ ጣፋጭ ድል ኢትዮጵያችንን በዓለም ፊት ‹ነፃ ሀገር› የተሰኘ የታሪክ ሜዳሊያ አጥልቃ ትኮራ ዘንድ ካባ ማጎናፀፉም ዓመታዊ ዝክሩ መቼም ቢሆን በቸልታ እንዳይታለፍ አድርጎታል፡፡ እናም እነዛን ባለውለታዎች ከታላቅ የክብር ሰላምታ ጋር እንዲህ ስል ላወድሳቸው እገደዳለሁ፡-

ዘላለማዊ ክብር ለዐድዋ ጀግኖች!!!
የፈራ ይመለስ!
እንግዲህ ጀግኖች አባቶቻችን በዚህ መልኩ ላለፉት ሶስት ሺህ ዘመናት ለነፃነታችን ሲዋደቁ ኖረዋል፡፡ በውጤቱም ነፃ ሀገር አስረክበውናል፡፡ ይሁንና ዛሬም እኛ ዘመነኛ ትውልድ ‹‹ነፃነት›› እያለን የምንጮኽለት ይህ ክቡር ጉዳይ ገና ምላሽ ላገኘም፡፡ በርግጥ ጥያቄው ከባዕድ ወረራና ተወራሪ ጋር የሚጋመድ አይደለም፤ ከሀገር ልጆች ጭቆና እንጂ፡፡ እንዲህ ‹ነፃነታችንን!› እያልን የምንጮኽለት መንፈስም፣ ወራሪውን ጣሊያን ያሸነፉ ቀዳሚ አባቶች ያላቆዩልን፣ ግን ደግሞ በጥያቄው ስም ጥተው፣ መልሰው መንፈሱን የጨፈለቁት ገዥዎቻችን የነጠቁንን መብት የሚወክል ነው፡፡ በአናቱም የትግሉ መንገድ በቅኝ ግዛት ለማሳደር በቀቢፀ-ተስፋ ተሞልቶ ወሰን የተጋፋው ጣሊያን ተሸንፎ ከተባረረበት ጋር ዝምድና የሌለው መሆኑን መረዳት ያሻል፡፡ ምክንያቱም ዘመነኛው የነፃነት ጥያቄ፣ እንደ ዐድዋው መድፍ አጓርቶ፤ መትረየስ የሳት-ላንቃውን ከፍቶ ሞት እየረጨ ሊፈታው አይችልምና ነው፡፡ ይህ አይነቱ የፋኖ መንገድ አንድም ጊዜው ያለፈበት ሲሆን፤ ሁለትም ህወሓት-ኢህአዴግን ለአራት ኪሎው ቤተ-መንግስት ቢያበቃውም፣ የታየው ለውጥ መለዮ ለባሽ ወታደርን፣ ገና ዝላዩን ባልጨረሰ የተማሪ አምባገነን ከመተካት አለመዝለሉ የአደባባይ ምስጢር ነው፡፡
ስለሆነም ዛሬ ጭቆናን የማሸነፊያ ብቸኛ መንገድ የፍርሃት ሰንሰለትን ሰባብሮ፣ በጨቋኞች ፍቃድ ለቆመው ስርዓትም ሆነ በድምፀ-አልባ ተወካዮቹ አጃቢነት ለፀደቁት ሕግጋት አለመታዘዝ ላይ የተመሰረተ ብቻ ነው፡፡ በእምቢተኝነት ደም-አልባ ሰላማዊ አመፅ የገዥዎችን ሰፈር ማራድ፤ እኩይ አላማዎቻቸውን የሚያስፈፅሙ ተቋማትን ጥርስ አልባ ማድረግ፤ አደባባዮችን በሰው ጎርፍ ማጥለቅለቅ፤ የትኛውንም አይነት ተቋማዊ ትብብርን መንፈግ፤ ኤፈርትና መሰሎቹን የንግድ ድርጅቶቻቸውን ማግለል፤ ሁሉም ፖለቲካዊ ፍላጎቶቻችን በኢትዮጵያዊ ዜግነት ስር እንደሚፈቱ ከልብ በማመን-ነገን ማለም፤ ለጥያቄው እስኪንበረከኩ ድረስ በሰላማዊው ተቃውሞ ፀንቶ መቆምንና መሰል ስልቶችን መተግበር ብቸኛ አማራጭ ነው፡፡ ይህ ይፈፀም ዘንድም በራስ ጉያ ፀለምት ለብሶ የተሸሸገ ፍርሃትን የተሻገሩ ጎበዛዝትና ወይዛዝርት ሊፈተኑበት፤ ከሽፈው የቀሩት ደግሞ ጥያቄውን በማጥላላትም ሆነ የተራራ ያህል በማግዘፍ ፍርሃትን አንብረው የአገዛዙን ዕድሜ ለማራዘም ደፋ-ቀና ከማለት ይታቀቡ ዘንድ የሚገደዱበት ዕለት ከደጅ መድረሱን ለመተንበይ ነብይ መሆንን አይጠይቅም፤ አይኖች-ያያሉ፤ ጆሮዎችም- ይሰማሉና፡፡
ግና፣ ይቺም ኑሮ ሆና እንዲህ የትውልድ ተጋሪዬ ጭሮ ግሮ ለማደር (አነስተኛና ጥቃቅንን ልብ ይሏል) በፖለቲካ አቋም እና በዘውግ ማንነት ተፈትኖ ማለፍ ግድ በሆነበት የሀገሬ ምድር፣ እውነት መመስከርን ስለምን በጀብደኝነት አንድምታ ታቃልለዋለህ? የተጠናወተህን ገደብ አልባ ፍርሃት፣ ለውጥ የሚጠይቁ ድምፆችን በማጣጣል ለመሸፋፈን መዳከር የት ያደርስሀል? የወላዋይ ብዕርህን ‹‹የለሁበትም!!›› ቅኔ ለበስ አቤቱታ እና ‹እውነት ለመናገር ጊዜና ቦታ አለው› የሚል ፍርሃታዊ ማምለጫህንስ ስለምን ለታናናሾችህ ለመጋት ትደክማለህ? በአገዛዙ መዝገበ-ቃላት ‹‹ፅንፈኛ፣ ጀብደኛ…›› ብለህ ማምታታትስ ባለፈ ዘመን ላይ መከተር አይደለምን? እውነት እውነት እልሀለሁም፡- በሰላማዊ መንገድ የስርዓት ለውጥን መጠየቅ፣ በ‹አትነሳም ወይ!› የሀገር ባለቤትነት ከፍታ ለአደባባይ ተቃውሞ ዘመነኞችን በእሪታ መጣራት፣ በየትኛውም የታሪክ ስፍር ጀብደኝነት ሆኖ አያውቅም፤ ለሕሊና መታመን እንጂ፡፡
በግልባጩ ነፃነትን ያህል ውድ ነገር የሚጠይቀውን ክቡድ መንፈስ ለማራከስ መሽቀዳደም፣ በንፁሀን ደም ከተጨማለቀው ጨቋኝ ገዥ የታማኝ ባለሟልነትን ማዕረግ ለማግኘት መባተል፣ ከዘመን መንፈስ ቀልባሽነት፣ በሞቀበት ከሚዘፍን ሆድ- አዳሪነት… ከቶስ ቢሆን በምን ይለያል? እመነኝ ‹ከአንድ እጅ ጣት በላይ የሚቆጠሩ ሀገራዊ የለውጥ ዕድሎች ስለምን ባከኑ ?› ብለህ ብታንሰላስል፤ ተጠያቂው የአገዛዙ አፈ-ሙዝ ብቻ አለመሆኑ ይገባሀል፤ ይልቁንም ሕዝብን በ‹ጎልያድ›፣ መንግስትን በ‹ዳዊት› መስለው የሚሰብኩ ሃሳዊያን ጻሐፍት ያነበሩት ታላቅ ፍርሃትም ድርሻ እንዳለው ትረዳለህና፡፡ ግና፣ ይህ ሁሉ ሆኖም አንድ ነገር እውነት ነው፤ ከገዘፈ የአመድ ተራራ ስር ፍንጥርጣሪ የጋሉ ፍሞችን የሚያገላብጥ ትውልድ እየመጣ ነው፡፡ ያን ጊዜም አንተን ዘንግቶ የትውልዱ መንፈስ ወካዮችን ብራና ላይ በክብር ይከትባል፡፡ ለነገሩ ቢዘገይም ታሪክ ከእውነት እንጂ ከፍርሃት ውል ኖሯት አያውቅም፡፡
የፈራ ይመለስ!
temesgen
ጥቂት ጉልበታሞች ለሚንደላቀ ጥቂት ጉልበታሞች ለሚንደላቀቁበት፣ ዘጠና ሚሊዮን ሕዝብ ለምን ይሰቃያል? ጭቆናን በዚህ ደረጃ ታግሶ መሸከምስ ከግዑዝነት በምን ይለያል? የወፍን ያህል የራስ ጎጆ መመኘት እንኳ እንደ ህብስተ መና በራቀበት ምድር፣ ግብር-ነጠቃን ባስከነዳበት ሀገር፣ ዜጎች በምርኮኛ ሕግ ተቀፍድደው ውለው በሚያድሩበት ክልል፣ መማር ድንጋይ ከመፍለጥ በማያሻግርበት ዘመን፣ የመኖርና ያለመኖር ግድግዳ ተደርምሶ ሁሉም ነገር ትርጉም የለሽ በሆነባት፣ ፍዘት፣ ቁዘማ ባረበበባት ኢትዮጵያ… ዝምታ ስንት ዘመን ይፈጃል? ኢህአዴግ እንዲህ በክፋት ጎዳና እየተመላለሰ፣ በጭካኔ በትር እያስገበረ፣ ፍትሕን የ‹አመፃ ድምፅ ማፈኛ›› አርጩሜ አድርጎ እያሴሰናት… ከሁለት አስርት በላይ ተደላድሎ እንዲቀመጥ ያደረገው የቀደሙት ትውልዶች ርግማን አይምሰልህ፤ አገር-ለበስ ፍርሃት እና ቸልተኝነት እንጂ፡፡ በአናቱም ስደት የስርዓቱ ማስተንፈሻ እንጂ የለውጥ ኃይል ሆኖ አያውቅምና ሲገፉህ- አትንደርደር፤ ሲያስሩህ-አትሸበር፤ ሲከሱህ-አትደንብር፤ ሲወነጅሉህ-አትሸማቀቅ፤ ሲያስፈራሩህ-አትደንግጥ፣ ሲያባራሩህ- አትሩጥ… ምክንያቱም ፍርሃትን የመስበሪያ ፅኑ አለት ይህ ብቻ ነውና፡፡ በተቀረ እነርሱ የሚለፍፉለት ‹‹ምርጫ›› ከአንድም አራቴ ሲያፋፍሩበት በመታየቱ ካለፈው ለውጥ ይኖረዋል ብለህ አትሞኝ፤ ከዚህ በኋላ ለውጥ ሊያመጣ የሚችለው ሰላማዊ እምቢተኝነት አንጂ፣ አባዱላ ገመዳን ተሸክሞት እስከመሮጥ ያደረሰው ያ የይስሙላ ኮሮጆ አይደለም፡፡ የኢኮኖሚ ዕድገትም ብቻውን የፖለቲካ ለውጥ አያመጣም፡፡ ዳሩ፣ ሲጀመርስ ዕድገቱ የት አለና?! ኢህአዴግ በነቢብ ‹መካከለኛ ገቢ ካላቸው ሀገራት ተርታ ለማሰለፍ አፋፍ ደርሻለሁ› በሚል ፕሮፓጋንዳ ቢያሰለቸንም፤ በገቢር አዳዲስ ምሬቶችን እያቆረ ስለመሆኑ በርካታ ማሳያዎችን መጥቀስ ይቻላል፡፡ ‹‹አደህይቶ ማዳከም!›› እንዲሉ ፕሮፌሰር መስፍን፣ ድህነትን የሚፈለፍሉ ኩሬዎችን በየመንደሩ ከመቆፈር ቸል ብሎ አያውቅም፡፡ ይሁንና የፍትህ መዛባት፣ ስራ-አጥነት፣ የመኖሪያ ቤት ችግር፣ መቆጣጠር የተሳነው የዋጋ ግሽበት፣ ማቆሚያ ያጣው የነዳጅ ዋጋ ጭማሪ፣ ባልተጠና እቅድ ተቆፋፍረው ከአገልግሎት ውጪ የሆኑ መንገዶች፣ አመቺ የስራ ቦታን በድርጅት የድጋፍና ተቃውሞ ሚዛን ማከፋፈል፣ አድሎአዊ አሰራር…
ብሶት የሚወልዳቸውን ነፃነት አብሳሪ አናብስት ጋላቢ ጀግኖችን ማበራከቱ አይቀሬ ነው፡፡ በአንድ ወቅት ዶ/ር መረራ ጉዲና ‹‹የራበው ሕዝብ መሪዎቹን ይበላል›› የሚል ቅድመ-ትንቢያ ቢነግረንም፣ ሰሞኑን የኢትዮጵያ አየር መንገድ አውሮፕላንን ጠልፎ ከመድረሻው ውጪ ያሳረፈው የኃይለመድህን አበራ ክስተት ደግሞ በአንፃሩ ርሃብን ያሸነፈው የማህበረሰብ ክፍልም ሰዋዊ ነፃነቱን ለማስረገጥ ሲል መሪዎችን ሊባላ እንደሚችል የሚያመላክት ነው፡፡ ይህ ሰው ማህበራዊ አክብሮትን በሚያጎናፅፍ ሙያ የተሰማራ ከመሆኑም በላይ፣ በኢትዮጵያ የሲቪል ሰርቪስ እርከን እጅግ ከፍተኛ ሊባል የሚችል ደሞዝ ተከፋይ ነው፡፡ ከዚህ አኳያም በአስከፊ ደረጃ የተንሰራፋውን የኑሮ ውድነት ለመቋቋም ብዙም እንደማይቸገር በድፍረት መናገር ይቻላል፡፡ ሀገር ቤት መኖር ካልፈለገም፣ ወደበለፀጉት ሀገራት ተሻግሮ ስራ ማግኘት እንደማይሳነው ያውቃል ተብሎ ይታሰባል፡፡ ግና፣ ይህ ሁሉ እውነት ቢሆንም የመረጠው መንገድ በራስ ላይ ቀድሞ ሊገመት
የማይችል አደጋ የሚጋብዝን ነው፡፡ እንግዲህ ከእነዚህ ተጨባጭ እውነቶች ተነስተን (እርሱ ራሱ ድርጊቱን የፈፀመበት ምክንያት ለስዊዘርላንድ ፍርድ ቤት እስኪናገር መጠበቁን ታሳቢ አድርገን) መላ-ምቶችን ማስቀመጥ እንችላለን ብዬ አስባለሁ፡፡ ለድርጊቱ በዋናነት መግፍኤ ተደርጎ ሊወሰድ የሚችለው አየር መንገዱ የገባበት ችግር ነው፤ ምክንያቱም ድርጅቱ በሂደት ህልፈቱን ወደሚያውጅበት መስቀል (ችንካር) እንዲያዘግም ገፊ ከሆኑ ጉዳዮች አስተዳደራዊ በደል የአንበሳውን ድርሻ ይይዛልና፡፡ አገዛዙ አንዳንድ የድርጅቱን ሰራተኞች በመዓት አይኑ ወደሚመመለከትበት ጠርዝ ያደረሰው ከዚህ ቀደም ‹በአውሮፕላኖቹ ላይ ባለኮከቡን ባንዲራ አትማለሁ› በሚል የፈጠረው አንጃ-ግራንጃ፣ በተወሰኑ ነባርና በጣም ወሳኝ ሰራተኞች ፊት-አውራሪነት በተቀሰቀሰ ተቃውሞ የተስተጓጎለበት ደረቅ እውነታ አንዱ ተደርጎ ይጠቀሳል፤ ሌላው ደግሞ ጠንካራና በሚገባ የተደራጃ የነበረውን የሰራተኛ ማህበር ለመቆጣጠር ያደረገውን ሙከራ ተከትሎ የገጠመው ተግዳሮት ነው (ዛሬ ማህበሩን ማስገበር መቻሉ ሳይዘነጋ)፡፡ እንዲህ አይነት ሕገ-መንግስታዊ ድፍረቶችን የስርዓቱ ኤጲስ-ቆጶሳት በቸልታ የሚያልፏቸው ባለመሆኑ፣ የተወሰዱት የማባረርና ከቦታ ዝቅ የማድረግ ፖለቲካዊ እርምጃዎች አየር መንገዱ ዛሬ ለደረሰበት ውድቀት መንገድ ከመጥረጉም በላይ፣ ተማራሪ ሰራተኞች እንዲበዙ አድርጓል፡፡ በአመክንዮ ድርጅቱ ከባለሙያ እጥረት (አቅም ማነስ) ጋር ብቻ ተያይዞ እየደረሰበት ያለውን ችግር ለመረዳት በስምንት ወር ውስጥ ብቻ ያጋጠመውን አራት ትላልቅ አደጋዎች ልጥቀስ፡- ካርጎ (Cargo MD-11F) አውሮፕላን ልምድ ያላቸው ኦፕሬተሮች በመባረራቸው፣ አዳዲሶቹ አበባ ለመጫን ሲሞክሩ በቆመበት ቦታ በቂጡ ወድቆ ጉዳት ደርሶበታል፤ ቦይንግ 767 (Boing 767) ከሞተር ጋር በተያያዘ ችግር ሮም ላይ ተገዶ አርፏል (በኋላ በተደረገለት ምርመራም ጥቂት ደቂቃዎች በአየር ላይ ቢቆይ ኖሮ ሊጋይ ይችል እንደነበረ ታውቋል)፤ ፎከር (Foker) አውሮፕላን ሞተሩ ተቃጥሎ ካርቱም ላይ አርፏል (ይህም ጥቂት ደቂቃ ቢዘገይ ኖሮ ተመሳሳይ አደጋ ይደርስበት እንደነበር ተነግሯል)፤ ቦይንግ 767-383 ኢ.አር (Boing 767-383 ER) ታንዛኒያ ውስጥ ማረፍ የነበረበትን ቦታ ስቶ፣ ትናንሽ አውሮፕላኖች የሚያርፉበት አሩሻ አየር ማረፊያ ለማረፍ ባደረገው ሙከራ በርካታ ኪሎ ሜትሮችን ተጉዞ ትልቅ የእርሻ ማሳ ውስጥ ሊቀረቀር ችሏል፡፡ እነዚህና መሰል ችግሮች ከኃይለመድህን አበራ እርምጃ ጋር ሲደማመሩ አየር መንገዱ ያለበትን ወቅታዊ ሁኔታ ለመረዳት ያስችላሉ፡፡
በአናቱም የጄኔቫው ክስተት የመሪዎቻችንን ውሸታምነት ከመቼውም በላይ የከፋ ደረጃ መድረሱን አሳይቶ አልፏል፡፡ ይኸውም የኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤትን በሚኒስትር ማዕረግ የሚመራው አቶ ሬድዋን ሁሴን፣ ጠለፋው በተሰማበት ሰዓታት ውስጥ ለሮይተር በሰጠው ቃለ-መጠይቅ ‹‹ድርጊቱን የፈፀሙት ካርቱም ላይ የተሳፈሩ አሸባሪዎች ናቸው›› ከማለቱ ጋር ይያዛል፡፡ ይህ ንግግር እንደቀላል ስህተት መታየት ያለበት አይመስለኝም፡፡ ምክንያቱም መንግስት በሀሰት ንፁሀንን ለማሰር ሲያሴር የሚሰጠው ሰበብ እንዲህ አይነት ፈጠራ መሆኑን ያስረግጥልናልና (ይህንን ጽሑፍ እያዘጋጀሁ ሳለሁ እንኳ በኢትዮጵያ ቴሌቭዥን የሰማሁት ዜና ሀገር ውስጥ ያሉ የተወሰኑ የግል ሚዲያዎችን ሁለት ኢምባሲዎች እንደሚያሽከረክሯቸው የሚወነጅል መሆኑ ተጨማሪ ማሳያ ይመስለኛል)፡፡ በርግጥ ስርዓቱ በከረባት ታንቀው የሀሰት ወሬዎችን ሚዲያ ፊት ቀርበው የሚያወሩ ደፋር ሚኒስትሮችን በብዛት መሰብሰቡ እውነት ቢሆንም፣ ከሬደዋን ሁሴን በፊት አቶ በረከት ስምኦን እንዲህ አይነት እጅና እግር የሌላቸውን ነጭ ውሸቶች ራሱ ከመጋፈጥ ይልቅ ብዙ ጊዜ በምክትሉ አቶ ሽመልስ ከማል በኩል ያስነግር እንደነበር ይታወሳል፡፡ ይሁንና በረከት ቦታውን ለሬድዋን ካስተላለፈ በኋላ በሬድዋንና ሽመልስ መካከል ያለው የፖለቲካ ጉልበት ያን ያህል የሚበላለጥ ባለመሆኑ፣ እንደቀድሞ ሁሉ ሬድዋን፣ በምክትሉ ለመጠቀም አስቸጋሪ እንደሆነበት ሰምቻለሁ (በነገራችን ላይ የአቶ ኃይለማሪያም ደሳለኝም ‹አለቃ እኔ ነኝ› የሚለው የሰሞኑ መከራከሪያ፣ እነበረከት-ደብረፅዮንን ከጣራ በላይ ሳያስቃቸው የሚቀር አይመስለኝም)
የሆነው ሆኖ ከላይ የተጠቀሱት ክስተቶች ከፍተኛ ደሞዝ የሚከፍል ድርጅት ሰራተኞችንም ያሳተፈ መሆኑን፤ በአምስት መቶ ብር አምስት ቤተሰብ ለማስተዳደር ከሚባትለው ኢትዮጵያዊ ጋር ካጋመድነው ሀገሪቱ ያለችበትን የፖለቲካ ክስረት፣ የኑሮ ውድነት ያነበረው ምሬት፣. አድሎአዊ አስተዳደር፣ መንግስታዊ ሙስና የደረሰበት አስከፊ ገፅታ፣ ተጠያቂነት ያሌለባቸው የፀጥታ ሰራተኞች የሚፈፅሙት ሕገ-ወጥ ተግባር፣ የአጠቃላይ መብት ጭፍለቃ… ተደማምረው መነሻና መድረሻው የታወቀውን የለውጥ ንቅናቄ መቀላቀልን ብቸኛ አማራጭ ያደርገዋል ብዬ አስባለሁ፡፡
የፈራ ይመለስ!
የስርዓቱ ልዝብ ተቃዋሚዎች ቀጣይ የሀገሪቱ ዕድል አብዮት ስለመሆኑ በተነሳ ቁጥር በግርድፍ ትንታኔ ሊነግሩን የሚሞክሩት ‹ኢትዮጵያ በ40 ዓመት ውስጥ ሶስት አብዮት ማስተናገድ አትችልም› የሚል ነው፡፡ ይሁንና ሙግታቸው ሁለት ግድፈቶችን ያዘለ ይመስለኛል፡፡ የመጀመሪያው የብሉይ አብዮትን መሰረታዊ ባህሪ ካለመረዳት ይነሳል፤ ዛሬም ድረስ የ66ቱን አብዮት አስመልክቶ የሚነሳው ተዋስኦ፣ ክስተቱ ብሉይ ማህበራዊ አብዮቶች ከሚባሉት መካከል እንደሚያስመድበው የሚያስረግጥ ነው፡፡ ይህ ስሌትም ብሉይ አብዮቶች ራሳቸውን በተለያዩ የዘመን ወቅቶች የመደጋገም ተጨባጭ ባህሪ እንዳላቸው ያመላክታል፡፡ እናም የሙግቱ ጥራዝ ነጠቅ አቀንቃኞች በዚህ ማዕቀፍ ውስጥ ከሚመደቡት መካከል ሩሲያና ፈረንሳይ በሁለትና ሶስት አብዮቶች ከመናጣቸው አኳያ ‹ኢትዮጵያንስ ምን ያህል የተለየች ሊያደርጋት ይችላል?› ለሚለው ጥያቄ በቂ መልስ የሚኖራቸው አይመስለኝም፡፡ በ66ቱ ከተነሱት ሁለት ዋነኛ (የመሬትና የብሔር) ጥያቄዎች፣ በ83ቱ ማህበረ- ፖለቲካዊ ሽግግርም ተነስተው አለመመለሳቸውን፣ ያሳለፍናቸው ሃያ ሁለት ዓመታት በበቂ ሁኔታ አስረጅ ናቸው፡፡ ይህ እውነታም ነው ሀገሬ ሶስተኛውን አብዮት ከማስተናገድ ውጪ የተሻለ ምርጫ እንዳይኖራት ያስገደደው፡፡
ሁለተኛው ጭብጥ በኢህአዴግ ስር ያዘገመችው ኢትዮጵያ ለአብዮት መነቃቃት የሚያበቁ ስርዓታዊ ክሽፈቶች መኖራቸውን ክዶ ከማለፍ ጋር የሚያያዝ ይሆናል፡፡ ለከተማ አብዮት መፈንዳት ወሳኝ ሆነው ከሚጠቀሱ ጭብጦች ብዙዎቹን የእኛይቷም ምድር እንደምታሟላ ከዚህ በፊትም ለማስታወስ ሞክሬያለሁ፡፡ በተለይም ሥራ-አጥ የተማሩ ከተሜ ወጣቶች አለቅጥ መብዛት እና ወጣቶች ከአጠቃላዩ ሕዝብ ወደ 37% የሚጠጉ መሆናቸውን ከአረቡ ፀደይ መንፈስ አኳያ ስንቃኘው አብዮቱን አይቀሬ ያደርገዋል፡፡ በአናቱም የሁለቱ ኃይማኖት ተከታዮች በመንግስት ላይ የያዙት የቅራኔ ልክ፣ የተቋጠረ የምሬት ፅንስ ስለመኖሩ በድፍረት ለመናገር ያስችላል፡፡ ለሁለት ዓመታት የዘለቀው የሙስሊሙ ጥያቄም፣ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የለዘበ ቢመስልም በሂደት እንደገና መቀስቀሱ አይቀሬ ነው፡፡ ምክንያቱም የእምነቱ ተከታዮች መሰረታዊ ጥያቄ የኃይማኖቱን ሙሉ ነፃነት መከወን ከመሆኑ ላይ ተነስተን፣ የተሰጠው መልስ መዋቅራዊ እንደነበረ ካስተዋልን ‹‹እንቅስቃሴው መለዘብ አለበት›› ያሉ ልሂቃንም ሳይቀሩ የነፃነቱ ጥያቄ በድጋሚ ተነስቶ መጅሊሱን እንዲነቀንቅ መፈለጋቸውን አምነን እንድንቀበል ያስገድደናል፡፡
ሌላው ጉዳይ የኦርቶዶክስ ኃይማኖት ተከታዮች ጉርምርምታ እና ማህበረ ቅዱሳን ላይ በሲኖዶሱ በኩል የሚካሄደው መንግስታዊ ጉንተላ፣ ምን ይዞ እንደሚመጣ ለመገመት የግድ ነገ ላይ መቆምን የማይጠይቅ መሆኑ ነው፡፡ በተጨማሪ ዛሬም5 እየተነሱ ካሉት የማንነት ጥያቄዎች አልፎ፣ በቅርምቱ ከአያቶቻቸው መሬት ከተፈናቀሉ ወጣቶች ምሬት ጋር የኢኮኖሚውን ድቀት አዛምደን ስንመለከት፣ ፍርሃትን አቸንፈው ወደኋላ ላለመመለስ የደፈሩ ወጣቶች ስርዓቱን እንደሚንዱት ለመመልከት ጥቂት ወራትን ብቻ መታገስ ይበቃል፡፡ ‹‹አብዮት የወይን ዘለላ ነው፤ እስኪበስል እንጂ መሬት እስኪወድቅ አትታገሰውም›› እንዲል ቼ ጉቬራ፤ ያረገዘውን አብዮት ከማዋለድ ያለፈ ምርጫ የለም፡፡
በድጋሚ ክብር ለዐድዋ ጀግኖች!!!

↧

የዋሽንግተንና የአዲስ አበባ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት እየተተቸ ነው

$
0
0

“በሙስና በእምነት ማጉደል በማታለልና በአመለካከት የሚለዩን ዝም በማሰኘት ሐይልን የያዛችሁ በተሳሳተ የታሪክ ገጽታ ላይ ነው ያላችሁት! ቡጢያቹን የምትፈቱ ከሆነ እጅ እንዘረጋላችሗለን” ያሉት ኦባማ አንባገነናዊ ቡጢያቸዉን ካልፈቱ…አንባገነናዉያን ጋር እጃቸዉን ዘርግተዉ ሲጨባበጡ መታየታቸዉ ትዝብት ላይ እየጣላቸዉ ነዉ!

Capitol
ዋሽንግተን ዲሲ፤ የካቲት 24/2006 (ቢቢኤን) ፦ የዩናይትድ እስቴትስ የዉጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት በኢትዮጵያ ዉስጥ ያለዉን ገደብየለሽ የሰብዓዊ መብት ጥሰት ለማመላከት ያደረጋቸዉን ጥናቶች ዋቢ በማድረግ በየካቲት 20/2006 ሪፖርቱን ይፋ አድርጓል።መሰረቱን አርሊንግተን ቨርጂኒያ ያደረገዉ ፖለቲኮ የሚባለዉ ጋዜጣ/መጽሔት የኦባማ አስተዳደር የኢትዮጵያ መንግስትን ከመሰሉ ለነጻነት ምቹ ካልሆኑ አገራት ጋር ያለዉ ምጸታዊ የዲፕሎማሲ ቁርኝትንም ይተቻል።

ከቀዝቃዛዉ ጦርነት ጀምሮ የዩናይትድ እስቴትስ መንግስታት ዜጎቻቸዉን ከሚጨቁኑ አገራት ጋር ግንኙነት ለመመስረት እምብዛም እንደማይጥሩ ፖለቲኮ እየገለጸ፤ለሚዛናዊነቱ ተስፋ የተጣለበት የኦባማ ካቢኔ ከሌሎቹ የዩናይትድ እስቴትስ ፕሬዝዳንቶች በባሰ መልኩ ለዜጎቻቸዉ ደህነነት ምቹ ካልሆኑ 25 አገራት ጋር ግንኙነት አለዉ ሲል የኦባማን የብሐራዊ ደህነነትና ጥበቃ አማካሪ የሆኑትን ሱዛን ራይስ ንግግርን በዋቢነት ያቀርባል። ራይስ “ግልፅ እንሁን አንዳንዴ እኛ አጥብቀን የምንይዛቸዉን ዉድ የሆኑ መብቶችን ከማያከብሩ መንግስታት ጋር የስራ ግንኙነት አለን” በማለት በባለፈዉ የነሐሴ ወር መናገራቸዉን ፖለቲኮ ይገልጻል።

ፖለቲኮ ለነጻነት የማይመቹ ብሎ ከጠራቸዉ 25 አገራት ዉስጥ ኢትዮጵያን በቁጥር 11 ላይ ያስቀመጠ ሲሆን ጠቅላይ ሚኒስቴር ሐይለማሪያም ደሳለኝ ይመሯታል የምትባለዋ ኢትዮጵያ የጸረ-ሽብር ህጓን ፖለቲከኞችን፣አክቲቪስቶችን፣መንግስትን ተጠያቂ የሚያደርጉ አካላትን ለማሰር እንደ ማህተም ትጠቀምበታለች ሲል ተጠያቂ ያደርጋል።ፖለቲኮ አክሎም የመለስ ዜናዊ አስተዳደር በ1999 ሶማሊያን በመዉረር እራሱን ለዩናይትድ እስቴትስ ግልጋሎት ማቅረቡንያስረዳል። ይህንንኑ አጋጣሚ በመጠቀም በአሜሪካ የሰለጠኑ የኢትዮጵያ ወታደሮች ከብሔር ብሔረሰቦች የተነሱ አማጺያንን ለማስቆም የጦርነት ወንጀል መፈጸማቸዉ በሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች ክስ ቢቀርብበትም ዋሽንግተን አዲስ አበባን በዲፕሎማሲ “እቅፍ-እቅፍቅፍ” እያደረገች መቀጠሏን ገልጿል።

ኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብትን ይጥሳሉ ከሚባሉት ጭቋኝ አገራት ጎራ ብትመደብም ፤እንደ አዉሮፒኣይኑ ቀመር በ2008 ብቻ ከዩናይትድ እስቴትስ 969 ሚሊዮን ዶላር በእርዳታ ተቀብላለች!

በኢትዮጵያ ዉስጥ ቀጣይ የሆነ የሰብዓዊ መብት ረገጣ፣ግድያ፣እስር፣የሐይማኖትነጻነትን መነፈግ፣የፕሬስ ነጻነት መመንመን፣የመማርና ማስተማር ሒደት ነጻነት በመንግስት መዳፍ ዉስጥ መግባት፣የመደራጀት-የመሰባሰብ-ሐሳብን በነጻ የመግለጽ ሁለንተናዊ መብት፣ የፍርድ ቤት አሰራር መበላሽትና በስልጣን መባለግን በመተንተን የዩናይትድ እስቴትስ የዉጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት በየካቲት 20/2006 አመታዊ ሪፖርቱን ይፋ አድርጓል። የኦባማ አስተዳደር አካል የሆነዉ የዉጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት አሳቃቂ የሆነ የመብት ረገጣ ኢትዮጵያ ዉስጥ መኖሩን እያወጀ የኦባማዉ ቤተ-መንግስት ኢትዮጵያን ከመሰሉ በአንባገነናዉያን ከሚመሩ አገራት ጋር “መለስ-ቀለስ” ማለቱ እያስተቸዉ ነው። የዉጭ ጉዳይ መስሪያ ቤቱን የሚመሩት ጃን ኬሪ አገራቸዉ ከስህተት የጠራች አለመሆኗን ያስረዳሉ።

“ዛሬ ስለ ሌሎች አገራት ያለዉ ሪፖርት ይፋ ለማድረግ ብንመጣም፤ እዚሁ አገራችን ላይ እራሳችንን በከፍተኛ መልኩ ተጠያቂ እናደርጋለን! እንከን የለሽ አለመሆናችንን እናዉቃለን” ጃን ኬሪ።

ጃን ኬሪ መስሪያቤታቸዉ ይፋ ያደረገዉ የሰብዓዊ መብት ሪፖርት ዋሽንግተን ዲሲ ባሉ የመስሪያ ቤቱ አባላት ጥናት ብቻ የተዘጋጀ ሳይሆን በእያንዱ አገራት ያሉ ኤምባሲዎችና ቆንስላ ጽ/ቤቶች ተሳታፊ መሆናቸውን ሲያስረዱ “በመላዉ አለም ያሉ ኤምባሲዎችና ቆንስላ ጽ/ቤቶች በጥናት እንደዚሁም እነዚህን ጽሁፎችን በመጻፍ አክቲቪስቶችን በመቅረብ መንግስታትን በማናገር የኤንጂኦና የሚዲያ ሪፖርቶችን በመተንተን አያሌ ሰአታትን አባክነዋል”ሲሉም ገልጸዋል።

ኬሪ ለነጻነትና ለመብት በሚደረግ ጥረት ዉስጥ ግለሰባዊ ሚና የጎላ መሆኑን መሆኑንም ይገልፃሉ።ከተለያዩ አገራት የለዉጥ ተምሳሊት የሚሏቸዉን ግለሰቦችን ስም በማንሳት የኢትዮጲያዉን ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ ሚናን አድንቀዋል “እስክንድር ነጋ ሐሳብን በነጻ ስለመግለጽ ኢትዮጵያ ዉስጥ የሚጽፍ ነው” ብለዋል።

በሚያዚያ 4/2004 የፔን አሜሪካን ሽልማትን ያገኘዉ እስክንድር ነጋ አለም አቀፋዊ ትኩረትን ያገኘ ኢትዮጵያዊ ጋዜጠኛ ነዉ። የኢትዮጵያ መንግስት በሽብር ፈጠራ ወንጅሎት ከመስከረም 3/2003 ጀምሮ በእስር ላይ ይገኛል።

የዩናይትድ እስቴስ የዉጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት ነጻነትን ከሚነጥቁ ጥቂቶች ጋር ሳይሆን ነጻነትን ከተነፈጉ ብዙሗን አጋር በመሆን አብሮ እንደሚቆም ኬሪ ቃላቸዉን እያደሱ ይናገራሉ “ዛሬ ቃላችንን በድጋሚ ለማረጋገጥ እንወዳለን! ክብርን ከሚነፍጉ ጥቂቶች ጋር ሳይሆን ክብርን ከሚሹ ብዙሗን ጋር አብረን ለመቆም ዝግጁ መሆናችንንም ለመግለጽ እንወዳለን!”በማለት ቢያስረዱም መንግስታቸዉ ከጨቋኝ አንባገነናዊያን ጋር በሚያደርገዉ ዲፕሎማሲያዊ ቅርርብ ተጠያቂ እየሆነ ነው።

በምርጫ ቅስቀሳ ወቅት ብዙ ቃልኪዳን የገቡት በራክ ኦባማ ቃሊኪዳናቸዉ አለተፈጸመም። በተመሳሳይ መልኩ ያሁኑ የዉጭ ጉዳይ መስራያ ቤት ሐላፊ ጃን ኬሪም ሆኑ የቀድሞዋ ሒላሪ ክሊንተን ከአንባገነናዊያን ጋር ያለዉን ግንኙነት ሲያደረጁ እንጂ ሲያመነምኑ አልተስተዋለም በማለት በርካታ ምሁራን፣ጋዜጠኞች እና የፖለቲካ ተንታኞች ወቀሳ ያቀርቡባቸዋል።

በጥር 12/2001 ቃለመሃላ የፈጸሙት ፕሬዝዳንት ኦባማ ሰላምና ክብርን ለሚሹ የአለማችን ዜጎች የርሳቸዉ መመረጥ ብስራት እንደሆነ አመላክተዉ ነበር። ከትላላቅ የአለማችን መዲናዎች ጀምሮ ወላጅ አባታቸዉ እስከመጡበት የኬኒያ መንደር የተስፋ ቃል ነበራቸዉ! እንዲም በማለት ስሜትን በሚነካ መልኩ ተናግረዉ ነበር…

“ከትላልቆቹ መዲናዎች እስከ አባቴ የተወለደባት መንደር ዛሬ ለሚመለከቱን ህዝቦችና መንግስታት፤ አሁን አሜሪካ የእያንዳንዱ አገር የእያንዳንዱ ግለሰብ ወዳጅ ናት! ሰላምና ክብርን ለሚፈልጉ ሴቶችና ህጻናት ዳግም ለመምራት ዝግጁ ነን” ፕሬዝዳንት በራክ ኦባማ።

ኦባማ ምንጫቸዉ ለሆነችዋ አፍሪካ ፕሬዝዳንታዊ ሐይላቸዉን በመጠቅም ያበረከቱት አስተዋፅኦ አናሳ ነዉ።ፕሬዝዳንቱ ቃለመሃላቸዉን ሲፈጽሙ ስልጣንን በማጭበርበር-በሙስናና የሐሳብ ልዩነትን በማፈን በሚቆናጠጡ አንባገነናዉያን ላይ ጣታቸዉን ቢቀስሩም ከነዚህ ምቹ ያልሆኑ አሳፍሪ መንግስታት ጋር እርሳቸዉም ይሁን ካቢኔአቸዉ ዲፕሎማሲያዊ ገደብን አለማበጀቱ አጠያያቂ እየሆነ ነዉ።

በአሜሪካዋ መዲና በዋሽንግተን ዲሲ ጥር 12/ 2001 ቀዝቃዉ አየር በጭብጨባ እየሞቀ ብዙዎች እያለቀሱ ኦባማ ለአንባገነናዊያን መልእክት አስተላልፈዋል።

“በሙስና በእምነት ማጉደል በማታለልና በአመለካከት የሚለዩን ዝም በማሰኘት ሐይልን የያዛችሁ በተሳሳተ የታሪክ ገጽታ ላይ ነው ያላችሁት! ቡጢያቹን የምትፈቱ ከሆነ እጅ እንዘረጋላችሗለን” ያሉት ኦባማ አንባገነናዊ ቡጢያቸዉን ካልፈቱ አንባገነናዉያን ጋር እጃቸዉን ዘርግተዉ ሲጨባበጡ መታየታቸዉ ትዝብት ላይ እየጣላቸዉ ነዉ።

ብዙ የተገቡ ቃልኪዳስኖች ተግባራዊ ሳይሆኑ በየካቲት 20/2006 ከዩናይትድ እስቴትስ የዉጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት የአመቱ የሰብዓዊ መብት ጥሰት ሲታወጅ “ከነጻነት ፈላጊዎች ጋር እንቆማለን!” የሚል ቃልኪዳን ተገብቷል።የዩናይትድ እስቴትስ መንግስት ባወጣዉ የሰብዓዊ መብት ሪፖርት የኢትዮጵያን መንግስት “ጨቋኝ-አፋኝ-አሳሪ-ገዳይ-ኢዲሞክራሲያዊ” መሆኑን ይፋ አድርጓል። ፖለቲኮ ጋዜጣ/መጽሔት ይህ ሪፖርት በወጣበት ማግስት የኦባማ አስተዳደር ኢትዮጵያን ከመሰሉ ለዜጎቻቸዉ ምቹ ካልሆኑ አገራት ጋር ይወዳጃል ሲል ይተቻል።

የዲሞክራሲ ተምሳሊት ነን የሚሉ የምእራቡ አገራት ለአንባገነናዊያን ዲፖሎማሲያዊ ከለላ መስጠታቸው የጥቅም ትስስር ወይስ ምጸታዊ የሆነ የዲፕሎማሲ ጨወታ? የሚለዉ ጥያቄ ቢነሳም …ትችቱእንደቀጠለ ነዉ።

↧

በአላሙዲ የሚደገፈው ፌዴሬሽን ዲሲን ጥሎ በሚኒሶታ የዘንድሮውን ዝግጅት ሊያደርግ ነው

$
0
0

“ዲሲን ለቀው መሄዳቸው ለእኛ ኢትዮጵያውያን ትልቅ ድል ነው”

-  በዲሲ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን

(በዲሲ አላሙዲንን ለመቃወም በከተማው ሲዘዋወር የነበረው መኪና ይህን ይመስል ነበር)
dem alamudi

(ዜና ትንታኔ) ሃገር ወዳድ ኢትዮጵያውያን የተሰባሰቡበትን ፌዴሬሽን ለሁለት ለመክፈል ተንቀሳቅሷል የሚባለው የወያኔ/ኢሕአዴግ ሥርዓት በአላሙዲ ስፖንሰርነት የሰሜን አሜሪካውን አመታዊ የስፖርት ፌስቲቫል ለመክፈል ቢጥርም ሃገር ወዳድ ኢትዮጵያውያን ነባሩን ፌዴሬሽን በማመከተል አሸናፊ መሆናቸው ባለፉት ሁለት ዓመታት በዳላስ እና በዋሽንግተን ዲሲ ታይቷል።

በሼህ መሃመድ አላሙዲ የሚደገፈውና የወያኔ ፌዴሬሽን እየተባለ የሚጠቀሰው aesaone ራሱን ተለጣፊ አድርጎ ሌሎች ኢትዮጵያውያን ዓመታዊ ዝግጅታቸውን በሚያደርጉበት ሳምንት ላለፉት 2 ዓመታት ሲያደርግ ባዶ ስታዲየም ከመታቀፍ ውጭ የሕዝብን ቀልብ ሊያገኝ እንዳልቻለ በግልጽ የታየ ጉዳይ ነው። እንደ ዋሽንግተን ፖስት ያሉ ሚዲያዎች ሳይቀሩ 2 ሚሊዮን ዶላር የወጣበት ዝግጅት የተገኘው ሰው ቁጥር ያስገርማል እስከማለት ዘግበው ነበር። ኢትዮጵያውያኑ ይህንን የአላሙዲ እግር ኳስ ቦይኮት በማድረጋቸው በስታዲየሙ ከሚገኘው ሰው ይልቅ ከውጭ ሆኖ የሚቃወመው ሰው ይበልጥ እንደነበር በተደጋጋሚ በሚዲያዎች መዘገቡም አይዘነጋም።

በሼህ አላሙዲ የሚደገፈው ፌዴሬሽን ለ3 ተከታታይ ዓመታት በዋሽንግተን ዲሲ የኳስ ውድድሩን እንደሚያደርግ ቀድሞ የገለጸ ቢሆንም፤ በተለይ አምና በዲሲ በተደረገው ዝግጅት ኢትዮጵያዊያኑ የአላሙዲ አፍ በደም ተጨማልቆ የሚያሳይ ፎቶ በትልቅ መኪና ተሰቅሎ በከተማዋ ሲንቀሳቀስ፤ አላሙዲ ባረፉበት ሆቴል አጠገብ ቆሞ ሲውል፤ ሆቴላቸው ውስጥ ሳይቀር ሕዝቡ አላሙዲንን እየተቃወመ የኳስ ውድድራቸውን “በደማችን ጨዋታ ይብቃ” በሚል ስያሜ በመስጠት ከተቃወማቸው በኋላ አላሙዲ ያልጠበቁት ጉዳይ ስለሆነ ወዲያውኑ ውድድሩን አቋርጠው ወደ መጡበት አፍረው እንደተመለሱ በወቅቱ በተለያዩ ሚዲያዎች ተዘግቧል።

አሜሪካ ያለን ኢትዮጵያውያን በገንዘብ አንገዛም፤ እኛ የደም ገንዘብ አንበላም፤ ከደም ገንዘብ ጋርም አንተባበርም በሚል ይህን የስፖርት ፌስቲቫል ቦይኮት ካደረጉ በኋላ የአላሙዲው ፌዴሬሽን ኳሱን ለ3 ዓመት ከከፈለበት የዋሽንግተን ዲሲው RFK ስታዲየም በመቀየር ወደ ሚኒሶታ እንደተዟዟረ የዘ-ሐበሻ ታማኝ ምንጮች አስታውቀዋል።

ከውስጥ አዋቂዎች መረጃ እንደተረዳነው አላሙዲ እንዲህ ያለ ተቃውሞ ይደርስብኛል ብለው ሳያስቡ በዋሽንግተን ዲሲ አፍረው ተመልሰዋል፤ ይህን ተከትሎም ዋናውን የኢትዮጵያውያን ፌዴሬሽኑ ገንጥለው የወጡትን አመራሮች ይኸው የአላሙዲ ፌዴሬሽን ያባረረ ሲሆን በዲሲ ላለፉት 2 ዓመት የታየውን ባዶ ስታዲየምና ተቃውሞ በሚኒሶታ አያጋጥመንም በሚል ኳሱ ዘንድሮ በሚኒሶታ ይደረጋል። በዚህም መሠረት ከጁን 29 እስከ ጁላይ 5 በሚኒሶታ ይህ ቶርናመንት እንደሚካሄድ ለማረጋገጥ ተችሏል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ በዲሲ የአላሙዲንን ኳስ ቦይኮት በማድረግ “ላለፉት 2 ዓመታት ያስተባበሩ ወገኖች ይህ ለኢትዮጵያውያን ትልቅ ድል ነው፤ የኛን ቦይኮት ፈርተው መፈርጠጣቸው ያስደስታል፤ በሚኒሶታም ተመሳሳይ ቦይኮት እንደሚገጥማቸው እንተማመናለን” በሚል በሶሻል ሚዲያዎች እየገለጹ ነው። እንደነዚህ አስተያየት ሰጪዎች “ለ3 ዓመት ኮንትራት ፈርመው በ2 ዓመታቸው ለቀው መውጣታቸው የኢትዮጵያውያን የትግል ውጤት ነው።”

↧
Viewing all 15006 articles
Browse latest View live