Quantcast
Channel: Ethiopian News | ዘ-ሐበሻ | Latest News Provider | News For All
Viewing all 15006 articles
Browse latest View live

የሲድኒ ኢትዮጵያዊያን የተሳካ የተቃውሞ ሰልፍ አደረጉ ( ከአቢይ አፈወርቅ )

$
0
0

አዲሱ አምባሳደር ሀፍረት ገጠማቸው

በአውስትራሊያ የኢትዮጵያ አምባሳደር የሆኑት አረጋ ሀይሉ ትላንት (ቅዳሜ ፌብሯሪ 22 ቀን) የሲድኒ ነዋሪ ኢትዮጵያዊያንን በልማት ዙሪያ ለማነጋገር የያዙት ፕሮግራም በአሳፋሪ ሁኔታ ተደመደመ።
ይህ በሜሪላንድ ሲቲ ካውንስል የተካሄደው ስብሰባ አምባሳደሩንና የስብሰባውን አስተባባሪዎች ጨምሮ በድምሩ 20 ሰዎች እንኳ ያልተገኙበት ሲሆን በርካታ ቁርጠኛ ኢትዮጵያዊያን ግን ለሰዓታት በአዳራሹ በር ላይ ቆመው ደማቅ የተቃውሞ ድምጽ ሲያሰሙ ውለዋል። ቪዲዮ ክሊፑን ለመመልከት
የውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር ዲያስፖራውን ለመከፋፈል ከዓመታት በፊት ያወጣውና በሲድኒም የአገዛዙ ወኪሎች ለረጅም ጊዜ የደከሙበት ዕቅድ ‹ውጤት አስገኝቷል› በሚል ያለአግባብ የተመኩት አምባሳደር አረጋ መላው የሲድኒ ነዋሪ እንዲገኝላቸው መወትወት የጀመሩት ከ2 ሳምንታት አስቀድሞ ነበር። ይሁንና የወገኖቻቸው ሰቆቃ እንደ የእግር እሳት የሚያንገበግባቸው የሲድኒ ነዋሪ ኢትዮጵያዊያን ግን ሳምንቱን ሙሉ ‹የስብሰባው አጀንዳ የዲሞክራሲ መታፈንና የሰብዓዊ መብቶች ረገጣ መሆን ይገባዋል› በሚል እርስ በርስ በስልክ የጸሁፍ መልዕክቶችና በሶሺያል ሚዲያዎች ኃሳብ ሲለዋወጡ ነበር የቆዩት። በዚህም የነዋሪው የቁጣ ልክ ከፍተኛ መሆኑ ድንጋጤ ውስጥ የከተታቸው አምባሳደር አረጋ ከስብሰባው አንድ ቀን አስቀድመው ለፖሊስ በመደወል ሀሳባቸውን መቀየራቸውንና በግል አዘጋጆቹ ከሚመርጧቸው ሰዎች በቀር ማንም ወደ አዳራሹ እንዳይገባባቸው ለመጠየቅ ተገደዋል።
New Picture (2)
ገና በመጀመሪያ ጉዟቸው በፈጸሙት የስሌት ስህተት ለሀፍረት የተዳረጉት አዲሱ አምባሳደር በይፋ የጋበዟቸውን ሰዎች ለማየት እንኳን ባለመድፈራቸው ከስብሰባው አንድ ሰዓት ዘግይተው ወደአዳራሹ በጓሮ በር ገብተዋል። ሰልፈኛውም በሳቅና በወረፋ ተሳልቆባቸዋል።
በስሜት ንዳድ የጋሉት ኢትዮጵያዊያን ከአዳራሹ በር ላይ ቆመው በከፍተኛ ድምጽ መፈክሮችና አገራዊ መዝሙሮችን ያሰሙ ነበር። ባኳያው ደግሞ እየተንጠባጠቡ ወደ ስብሰባው በማምራት ላይ ከነበሩ አናሳ ቁጥር ያላቸው ደጋፊዎች መሀል አንዳንዶቹ የተቃውሞውን ጥንካሬ በመመልከት ከቅርብ ርቀት ፊታቸውን እያዞሩ ሲመለሱ ታይተዋል።
የአገዛዙ ወኪሎች ‹ለተለያዩ ጥቅማጥቅሞች ይሸነፋሉ› በሚል የገመቷቸውን ኢትዮጵያዊያን በማባበልና በመደለል ለረጅም ጊዚያት የደከሙበት ይህ ዝግጅት፤ ነባር የህወሀት ደጋፊዎችን፣ አምባሳደሩንና የዝግጅቱን አስተናባሪዎች ጨምሮ 20 የሚሞሉ ሰዎችን እንኳ ማሰባሰብ ያለመቻሉ ለኤምባሲው ሀፍረትን፣ ለተቃዋሚዎች ደግሞ እርካታን ሊያጎናጽፍ በቅቷል።
በሚያስተዛዝብ ደረጃ አብዛኞቹ ታዳሚዎች ከተመሳሳይ ብሄር የፈለቁ ቢሆኑም ተቃዋሚዎቹ ግን እየደጋገሙ “እናንተ የትግራይን ብሄር አትወክሉም!” “የትግራይ ተወላጅ ወገኖቻችን የአገር ፍቅርን የሚያውቁ ኩሩዎች ናቸው። እናንተ ግን ሆዳሞች ናችሁ።” ሲሏቸው ተደምጠዋል። አስገራሚ የአቋም ለውጥ አድርጋ ‹ዓይንሽ ለዓፈር› የተባለችውን አርቲስት አይናለም ተስፋዬን ጨምሮ አራት ያህል የሌላ ብሄር ተወላጆችም ወደ አዳራሹ ሲገቡ ታይተዋል።
New Picture
ከስብሰባው ታዳሚዎች በቁጥር ከአራት እጥፍ በላይ የሚልቀውና አንገቱን ቀና አድርጎ በከፍተኛ የስሜት ንዳድ ድምጹን ሲያሰማ የቆየው ተቃዋሚ ከያዛቸው መፈክሮች መሀል ፦”ያለ ዲሞክራሲ ልማት የለም” “የጸረ ሽብር አዋጁ ሽብር ማራመጃ ነው።” “የመሬት መቀራመቱ ይቁም!” “በኢህአዲግ ፖሊሲ ሙሰኞች እንጂ አገር አይለማም” የሚሉና ሌሎችም ይገኙበታል። በግፍ እስር ላይ የሚገኙት ንጹሀን የህዝብ ልጆች እነ ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋም በጋለ ስሜት ሲጠቀሱ ውለዋል።
ባስመዘገቡት ውጤት እርካታ የተሰማቸው የአገዛዙ ተቃዋሚ ኢትዮጵያዊያን የዕለቱን ተልዕኳቸውን አጠናቀው ወደ የቤታቸው ከመመላሳቸው በፊት በአገራቸው ጉዳይ ከመቼውም በላይ የተጠናከረ እንቅስቃሴ ማድረግ እንደሚገባቸው ተወያይተዋል። መልካም ትብብርና ወንድማዊ ስሜት ያልተለያቸው የአውስትራሊያ ፖሊሶችም ልባዊ ምስጋና የቀረበላቸው ሲሆን እነሱም በአጸፋው ሰልፈኛው ሰልፉን በፍጹም ጨዋነት በማካሄዱ ምስጋና አቅርበውለታል። ይህን የተሳካ የተቃውሞ ሰልፍ በአጭር ጊዜ ውስጥ በሚያኮራ ቅንጅት ያስተናበሩት የሰልፉ አዘጋጆችም ተገቢው አክብሮት ተችሯቸዋል።
ኤንባሲው የበተነውን የጥሪ ደብዳቤ ከታች ይመልከቱ!

New Picture (3)


ዛሬ በባህርዳር ሕዝቡ በባዶ እግሩ አደባባይ የወጣበት ታሪካዊ ሰላማዊ ሰልፍ (ዜና ፎቶ)

ዛሬ በባህርዳር የተጠራው ሰላማዊ ሰልፍ በሰላም ተጠናቀቀ፤ ሕዝቡ በባዶ እግሩ በመውጣት በብአዴን/ኢሕአዴግ ላይ ቁጣውን ገለጸ

$
0
0

bahr dar 18
(ዘ-ሐበሻ) የአማራው ክልል ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ አለምነው መኮንን የሚመሩትን የአማራ ሕዝብ በጸያፍ ቃላት መሳደባቸውን ተከትሎ አንድነት እና መኢአድ ፓርቲዎች በጋራ በባህርዳር ዛሬ በባህርዳር የጠሩት ሰላማዊ ሰልፍ ከፍተኛ የሆነ ሕዝብ በተገኘበት በሰላም ተጠናቀቀ። “ህዝቡ ከባዶ ጭንቅላት ባዶ እግር ይሻላል” ሲል ለብአዴን/ኢህአዴግ ተቃውሞን አሰማ።

በ10 ሺህዎች የሚቆጠሩ የባህርዳር ነዋሪዎች ቁጣቸውን ለመግለጽ በወጡበት በዚህ ሰላማዊ ሰልፍ ሕዝቡ በአቶ አለምነው የተሰደበውን ለማስታወስና ቁጣውንም ለመግለጽ በባዶ እግሩ እንደነበር ከስፍራው መረጃ ያደረሱን የዘ-ሐበሻ ተባባሪዎች ገልጸዋል። “ሰልፈኛው ጫማውን አንገቱ ላይ በማንጠልጠል በሰላማዊ ሁኔታ በባዶ እግሩ በመሄድ በአዲስ የተቃውሞ ስልት ድምጹን አሰምቷል” ያሉት በስፍራው የነበሩ የሰልፉ ታዳሚዎች እንዲህ ያለው የትግል አገላለጽ የሚደነቅና ወደፊትም ሊበረታታ የሚገባው ነው ብለዋል።

ባህር ዳር በፖሊስና የፀጥታ ሃይሎች በከፍተኛ ሁኔታ ተሰራጭተው የዋሉ ሲሆን ከከተማዋ አጎራባች አካባቢዎች ጭምር የተሰባሰቡት ልዩ ሃይሎችና የክልሉ ፖሶች በነዋሪው ላይ ውጥረት ለመፍጠርና በሰልፉ እንዳይሳተፍ በከፍተኛ ሁኔታ ቢሞክሩም ሕዝቡ ግን በአቶ አለምነውና በብአዴን ላይ ቁጣውን ከመግለጽ አላገደውም ያሉት የዘ-ሐበሻ ዘጋቢዎች “ወያኔ ለውድቀቷ አማራን ትሳደባለች” በሚል ቁጣ ካለምንም ፍራቻ አደባባይ ወጥተዋል ብለዋል።
Bahr dar 6
በተለይ ኢሕአዴግ በባህር ዳር ከተማ ሕዝቡ ሰልፍ እንዳይወጣ በ5ለ1 ጠርናፊና ተጠርናፊዎች “ሰልፉ ተሰርዟል” የሚል ሃሰተኛ ወሬ በማውራት ሕዝቡን ለማደናገር መጣሩን የገለጹት የዘ-ሐበሻ ዘጋቢዎች የአንድነት እና የመኢአድ መሪዎች እስከመጨረሻው ሰዓት ድረስ በመኪና እና በ እግር በመሄድ ሕዝቡን በመቀስቀስ የዛሬውን ሰልፍ ለስኬት አብቅተውታል ሲሉ ዘግበዋል። በተለይም የከተማዋን የባጃጅ ሾፌሮችን በማህበራቸው አማካኝነት ኢሕአዴግ ሰብስቦ ይህን ሰልፍ የምታጅቡ ከሆነ ፈቃዳችሁን ትቀማላችሁ የሚል ማስፈራሪያ ቢደርስባቸውም አቶ አለምነው አማራውን ከሰደቡት ስድብ አይበልጥም በሚል ባጃቻቸውን አስቀምጠው ሰልፉን መቀላቀላቸውን ዘጋቢዎቻችን ገልጸውልናል።
bahr dar 4
በባህር ዳር በተደረገው በዚህ ትልቅ የተቃውሞ ሰልፍ ላይ አቶ አለምነው በአማራ ህዝብ ላይ የተናገሩት የጥላቻ ንግግር በትላልቅ ስፒከሮች ለሰልፈኛው በድጋሚ የተሰማ ሲሆን ሰልፈኛውም በቁጭት በብአዴን ላይ ተቃውሞውን በአንድ ድምጽ አሰምቷል።

“ገበሬው በገዛ መሬቱ ስደተኛ አይሆንም”

“ክብራችንን የደፈሩት የብአዴን አባላት ለፍርድ ይቅረቡ”

“ነፃነታችን በእጃችን ነው”

ህዝቡ ከባዶ ጭንቅላት ባዶ እግር ይሻላል”
“የመሬት ቅርምቱ ይቁም”

“አማራውን ከሌላው ኢትዮጵያዊ ጋር ለመለየት የሚደረገውን የኢሕ አዴግ ሴራ በጥብቅ እናወግዛለን”

“ብአዴን/ኢሕአዴግ አማራውን የመምራት የሞራል ልእልና የለውም የለውም”

“ሕዝብን ከእርስቱ ማፈናቀል ይቁም!”

የሚሉና አቶ አለምነው ለፍርድ እንዲቀርቡና ይቅርታ እንዲጠይቁ የሚጠይቁ መፈክሮች በዛሬ ፌብሩዋሪ 23 ቀን 2014 ሰልፍ ላይ ተሰምቷል።

በባህርዳር ግሽ አባይ/ ቀበሌ 12 የሚገኘው አንድነት ፓርቲ ጽ/ቤት መነሻውን አድርጎ ከጠዋቱ 3 ሰዓት ጀምሮ የተጀመረው ይሄው የተቃውሞ ሰልፍ ከግሽ አባይ/ ቀበሌ 12 ተነስቶ በድብ አንበሳ አካባቢ ዞሮ ወደ ክልሉ መስተዳድር ጽ/ቤት ያመራ ሲሆን በሰልፉ ላይ ንግግር ያደርጉት የአንድነት ፓርቲ ሊቀመንበር ኢንጂነር ግዛቸው አቶ አለምነው መኮንን ይቅርታ የማይጠይቁና ከስልጣናቸው የማይወርዱ ከሆነ ፓርቲያቸው በድጋሚ በባህርዳር የተቃውሞ ሰልፍ እንደሚጠራና ባለስልጣኑን በፍርድ ቤት እንደሚከስ አስታውቀዋል። የህዝቡን ከፍርሃት መላቀቅ ያደነቁት ኢንጂነር ግዛቸው በሰላማዊ ሰልፉ ላይ የተገኘውን ሕዝብ አመስግነዋል። በተጨማሪም በዚህ ሰልፍ ላይ የመኢአድ ፕሬዝዳንት አቶ አበባው መሃሪ ንግግር አድርገዋል። አቶ አበባው በንግግራቸው አቶ አለምነው መኮንን በህግ እንዲጠየቅ፣ ብአዴን የአማራ ህዝባ ወኪል ነኝ ማለቱን እንዲያቆምና አቶ አለምነው መኮንን የአማራን ህዝብ ይቅርታ እንዲጠይቁ አስረግጠው ተናግረዋል።

የሰልፉን ፎቶዎች ለማየት እዚህ ይጫኑ

ረዳት ፓይለቱ ኃይለመድህን አበራን በመደገፍ በስዊዘርላንድ ሰላማዊ ሰልፍ ተጠራ

$
0
0

(ዘ-ሐበሻ) የኢትዮጵያ አየር መንገድ አውሮፕላንን ወደ ስዊዘርላንድ አቅጣጫ አስቀይሮ የዓለም መነጋገሪያ የሆነው ረዳት አብራሪ ሃይለመድህን አበራን በመደገፍ፤ የስዊዘርላንድ መንግስት አብራሪው የጠየቀውን የጥገኝነት ጥያቄ እንዲቀበለው ለመጠየቅ በስዊዘርላንድ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ሰላማዊ ሰልፍ ጠሩ። አርብ ፌብሩዋሪ 28 ቀን 2014 በበርን  ከ12 ሰዓት ከ30 ጀምሮ ይደረጋል በተባለው በዚሁ ሰልፍ ላይ “የሃይለመድህን ድምጽ የኔም ድምድ ነው” በሚል መርህ እንደሚደረግ የሰልፉ አስተባባሪዎች ለዘ-ሐበሻ በላኩት በራሪ ወረቀት ላይ አስታውቀዋል። በዚህ የድጋፍ ሰልፍ ላይ ሁሉም ኢትዮጵያዊና የኢትዮጵያ ወዳጆች እንዲገኙም ጥሪ ቀርቧል።
ሃይለመድህን አውሮፕላኑን ወደ ስዊዘርላንድ ጠልፎ ካሳረፈው በኋላ ይህን ዜና የዘገቡ የውጭ ሚዲያዎች በአብዛኛው በኢትዮጵያ ያለውን የሰብአዊ መብት ጥሰት አብረው ዘግበዋል። የአውሮፕላን ጠለፋውንም ከዚሁ የሰብአዊ መብት አለመከበር ጋር አያይዘው ብዙ መዘገባቸው ይታወሳል።

የሰልፉ በራሪ ወረቀት (ፍላየር) የሚከተለው ነው።
Hailemedhin

“ከማጥናት በቀር ሌላ ነገር የማያውቁ፤ የተስተካከሉ ልጆች ነው ያሉን”–ከኃይለመድህን አበራ እናት ጋር የተደረገ ቃለ ምልልስ!!

$
0
0

ethio airlines
ረዳት አብራሪ ኃይለመድህን አበራ ባለፈው ሳምንት፤ ሲያበር የነበረውን የኢትዮጵያ አየር መንገድ አውሮፕላን ጄኔቭ ማሳረፉ የሚታወስ ነው። ከአብራሪው ጋር በተያያዘ እስካሁን እህቱ እና መንድሙ የየራሳቸውን ሃሳብ እና አስተያየት ሰጥተዋል። አሁን ደግሞ ከ እናታቸው ጋር የተደረገውን ቃለ ምልልስ ይዘን እንቀርባለን። ቃለ ምልልሱን በድምጽ ያደረገው ዳዊት ሰለሞን ነው። ባህርዳር ላይ የተደረገውን ሰላማዊ ሰልፍ ለማስተባበር በስፍራው ተገኝቶ ነበር። እናም ይህን አጋጣሚ በመጠቀም ቃለ ምልልስ አድርጎላቸዋል። በመግቢያውም ላይ እንዲህ የሚል ማስታወሻ ጽፏል። “በባህርዳር ቆይታዬ ከሰሞኑ ዋነኛ የመነጋገሪያ ርዕስ ከሆነው ረዳት ፓይለት ሃይለመድህን አበራ ወላጅ እናት ጋር ለጥቂት ደቂቃዎች የመገናኘት እድል ተፈጥሮልኝ ነበር፡፡ እናትየው የወንድማቸውን አርባ አውጥተው ከሩቅ ቦታ መመለሳቸው በመሆኑ ድካም ቢነበብባቸውም ለማቀርብላቸው ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት አላመነቱም፡፡ ምስጋናዬን እያቀረብኩ ልጃቸውን የተመለከተ መልካም ዜና እንዲያደምጡ ጸሎቴ ነው::” ብሏል።

ቃለ ምልልሱን ያደረገው – ዳዊት ሰለሞን
ወደ ጽሁፍ የመለሰው – ዳዊት ከበደ ወየሳ

ቃለምልልሱን ለማንበብ እዚህ ይጫኑ

በቦሌ የባንክ ጥበቃው ለጥበቃ በተሰጠው ጠመንጃ ራሱን በጥይት መትቶ ገደለ

$
0
0

bole

ከጽዮን ግርማ – አዲስ አበባ

በሱፍቃድ በጋሻው የተባለ ዕድሜው በሃያ አራት ነው፡፡ አሁን የአዲስ አበባ ነዋሪ ሲኾን የመጣው ግን ከአማራ ክልል አካባቢ መኾኑን የቅጥር መዝገቡ ያሳያል፡፡ በቦሌ መንገድ ላይ ከአራት ጊዜ በላይ በተከታታይ ወደ ሰማይ ከተኮሰ በኋላ ራሱን አጠፋ፡፡ ቦሌ መንገድ ሚሊኒየም አዳራሽ አካባቢ በሚገኝ የሕብረት ባንክ ቅርንጫፍ በጥበቃ ሥራ ላይ የነበረው ወጣቱ በሱ ፍቃድ ለምሳ ተቀይሮ ሲገባ ከሥራ ባልደረባው ላይ የተቀበለውን የጥበቃ መሣሪያ ተቀብሎ ለጊዜው ምን እንደኾነ ያልታወቀ(እስካሁን እኔ ያላወኩት) ነገር እየተናገረ እየሮጠ ወደ ሰማይ በመተኮስ በግምት ወደ አራት ጊዜ ያህል ከተኮሰ በኋላ አገጩ ላይ አስደግፎ ወደ ጭንቅላቱ በመተኮስ ራሱን አጥፍቷል፡፡ በአሁኑ ሰዓት አስክሬኑን ሰማያዊ የሚበዛበት ዥንጉርጉር ጨርቅ ሸፍነውት መንገድ ላይ ተኝቷል፡፡ የደንብ ልብሱን እደለበሰ ሲኾን አጠገቡ በጥይቱ የተበሳ ኮፍያው ወድቋል፡፡ የጭንቅላቱ ስጋ እና አጥንቶቹ ተበታትነዋል፡፡ በሱፍቃድ አጋር የተባለው የጥበቃ ሥራ የሚሠራ ኤጀንሲ ተቀጣሪ መኾኑን እና ሕብረት ባንክ ከመጣ ሁለት አካባቢ እንደኾነው የሥራ ባልደረቦቹ ነግረውኛል፡፡አሁን በተገኘ መረጃ ‹‹ኑሮ መኖኛል›› ሲል ተሰምቷል፡፡ እዛ አካባቢ ያሉ ፖሊሶች ደግሞ በምን እንዳወቁ አላውቅም ከቤተሰቡ ተጣልቶ ነው ብለዋል፡፡

ዘ-ሐበሻ ተጨማሪ መረጃዎችን እያፈላለገች ነው – እንደደረሰን እንመለሳለን።

Hiber Radio: በቤይሩት ቦንብ ፍንዳታ ኢትዮጵያዊቷ ሕይወቷ አለፈ

$
0
0

የህብር ሬዲዮ የካቲት 16 ቀን 2006 ፕሮግራም

ጋዜጠኛ ሃብታሙ አሰፋ

ጋዜጠኛ ሃብታሙ አሰፋ

<... ...>

አክቲቪስት መስፍን አስፋው ከዋሽንግተኑ የድጋፍ ሰልፍ አስተባባሪዎች አንዱ ለህብር ከሰጠው ቃለ መጠይቅ

> የመኢአድ ሊቀመንበር አቶ አበባው መሐሪ በባህር ዳር ለተቃውሞ ለወጣው ሕዝብ ካደረጉት ንግግር

>

ኢ/ር ግዛቸው ሽፈራው የአንድነት ፓርቲ ሊቀመንበር በባህር ዳር ለተሰበሰበው ሕዝብ ካደረጉት ንግግር የተወሰደ(ዘገባውን ያዳምጡ)

የረዳት አብራሪው መጪው ዕጣና ከዚህ በፊት በአውሮፕላን ተደብቆ ቤልጂየም የገባው ኢትዮጵያዊ እንዴት በስርዓቱ ማጭበርበር ተላልፎ ተሰጠ?( ወቅታዊ ዘገባ ይዘናል)

የኦጋዴን ነጻ አውጭ ግንባር እና የህወሃት በሸር የተወጠነ ድርድር ሲቃኝ(ክፍል ሁለት)

ሌሎችም ዝግጅቶች

ዜናዎቻችን

- ስዊዘርላንድ ከአገሯ ረዳት አብራሪዎን አሳልፋ እንዳትሰጥ እየተጠየቀ ነው

- ነገ በዲሲና በፍራንክፈርት አርብ በስዊዘርላን የአገሪቱን መንግስት ለመጠየቅ ሰልፍ ይደረጋል

- ኦብነግ ሰሞኑን ሰባት የኢትዮጵያውን አገዛዝ የጸጥታ ሰዎችን ገደልኩ አለ

- በባህር ዳር ነዋሪዎች ከባዶ ጭንቅላት ባዶ እግር ይሻላል ሲሉ ታላቅ የተቃውሞ ሰልፍ አደረጉ

- የአማራን ብሔር የተሳደቡ የክልሉ ም/ል ፕሬዝዳንት ለፍርድ እንዲቀርቡ ተጠየቀ

* ለተቃውሞ ሰልፍ የወጡ ገበሬዎች ታስረዋል

- ሱዳን ውስጥ በወረበሎች የተደፈረች ኢትዮጵያዊት ትፋተኛ ተባለች

- በቤይሩት ቦንብ ፍንዳታ ኢትዮጵያዊቷ ሕይወቷ አለፈ

- በሚኒሶታ የሚኖሩ የኦሮሞ ማህበረሰብ ዘርፈ ብዙ የሆነ ድህረ ገጽ ሊከፍቱ ነው

በቬጋስ የየካቲት 12 የሰማዕታት ቀን ተከበረ

ሌሎችም ዜናዎች አሉ

በባህር ዳር ከተማ የተደረገው ሰላማዊ ሰልፍ እድምታ (በገዛኸኝ አበበ ኖርዌይ )

$
0
0

እባካችው እናንተ የፖለቲካ መሪዎች አንድ ሆናችው ሕዝቡን ለለውጥ አነሳሱት
gezahegn abebe
ይቼን ን አጠር ያለች ጹሁፍ እንድጽፍ ያነሳሳኝ በትናትናው እለት የካቲት 16 2006 ዓመተ ምህረት የአማራ ክልል በሆነችው በባህር ዳር ከተማ አንድነት ለፍትህና ለዲሞክራሲ (አንድነት) ፓርቲ እና መላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ) በቅርቡ የብአዴን/ኢህአዴግ ዋና ፀሐፊ እና የአማራ ክልል ምክትል ፕሬዘዳንት አቶ አለምነው መኮንን የአማርን ሕዝብ በማዋረደ እና በማናናቅ በአማራ ሕዝብ ላይ የተናገሩትን ስነ ምግባር የጎደለው ንግግራቸውን በመቃወም የጠሩትን በደማቅ ፣ ደስ በሚል እና በሚያኮራ ሁኔታ የተጠናቀቀውን ታላቅ ሰላማዊ የተቃውሞ ሰልፍ በቪዲዩ ከተመለከትኩኝ በኋላ ነው::

ይህ በትናትናው እለት ተካሂዱ በነበረው የሰላማዊ ተቃውሞ ሰልፍ ላይ የባህር ዳር ከተማ ሕዝብ በተለይም ወጣቱ የህብረተሰብ ክፍል ሆ ብሎ በነቂስ በመውጣት እልህና ወኔ በተሞላበት ትህይንት ማንነቱን በገሀድ ያስመሰከረበት የተቃውሞ ሰልፍ እንደነበር ተመልክቻለው:: ወጣቱ ትውልድ ላይ ቁጭት ፣ ንዴት፣ እልህ እና ወኔ ይታይበታል የወያኔ የጭቆና እና የዘረኝነት አገዛዝ አማሮታል፣ ለውጥንም እንደሚፈልግ በአደባባይ በመጮህ እየተናገረ ይገኛል:: የመለው የኢትዮጵያ ሕዝብ ምሬት እና ብሶት ኢህአዲግ እና የኢትዮጵያ ሕዝብን ሆድ እና ጀርባ እንዲሆኑ አድርጓቸዋል:: ሕዝቡም ከምሬቱ እና ከብሶቱ ብዛት የተነሳ ወኔን እና ድፍረትን በተላበሰ መንገድ ነበር የተቃውሞ ድምጹን ሲያሰማ የዋለው ::
bahr dar 4
ሕዝቡ በነቂስ ወቶ በድፍረት የተቃውሞ ድምጹን እንዲያሰማ የአንድነት እና የመኢአድ አባላትም ሆነ አመራሮች በአንድነት በመሆን የሰሩት ስራ የሚያስመሰግናቸው እና የሚያኮራ ተግባር ሲሆን ለሌሏቹም የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች ትምህርት ሊሆን ይገባል እላላው :: የኢትዮጵያ ሕዝብ ለውጥን ይፈልጋል::ስለዚህም ለለውጥ እና ለትግል የሚያነሳሳው ቀስቃሽ አመራርን ይፈልጋል ::ይህን ለውጥ የናፈቀውን እና ነፃነት የናፈቀውን ሕዝብ ለለውጥ ትግል ማነሳሳት የተቀዋሚ ፓርቲ ድርጅቶች ተግባር እና ኀላፊነት መሆን ያለበት ጉዳይ ይመስለኛል :: የተቃዋሚ የፖለቲካ ፖርቲ ድርጅቶች አንድ ሀሳብ ይዘው በአንድ ራዕይ እና ትግል ወያኔን ለመጣል እና ከስልጣኑ ለማስወገድ ሰላማዊ የተቃውሞ ሰልፎችንም ሆነ ማንኛውንም የሰላማዊ ትግል እንቅስቃሴዎችን ለማድረግ ቢተባበሩ እና ሕዝቡን ቢያነሳሱት ለውጥን ናፋቂው የኢትዮጵያ ሕዝብ በምንም ሁኔታ ውስጥ በማለፍን እና ትግሉ የሚጠይቀውን ማንኛውንም መስዋዕትነት ለመክፈል ባገኛው አጋጣሟ ሁሉ ቆራጥቱን እያሳየ እና እያስመሰከረ ይገኛል::

ይህንንም የወያኔ ካድሬዎችም ሆነ ባለስልጣኖች ጠንቅቀው የሚያቁት እና አሳሳቢ ጉዳይ የሆነባቸው ይመስለኛል :: ለዚህም ነው በተለያየ መንገድ በሕዝቡ ላይ የአካልም ሆነ የስነልቦና ጥቃት እያደረሱ የሚገኙት በህዝቡ ላይ እየደረሰ ያለው የአካልም ሆነ የስነልቦና ጥቃትእንዳለ ሆኖ ወያኔዎች ወጣቱን ለመከፋፈል በተለያየ ጥቅማጥቅም በማታለለ ለመያዝ እየሞከሩ ይገኛሉ:: ነገር ግን ለሆድ እና ለጥቅማ ጥቅም አልገዛም፣ ለወያኔም ካድሬዎች አላጎበድድም የሚለውን ወገን፤ የዚያ ድርጅት አባል የዚህ ድርጅት ደጋፊ እያለ ተለጣፊ ስም በመስጠት ከትምህርት፤ ከስራ እያፈናቀሉት፤ እያሰሩት፤ እያንገላታቱ ያሉት። ወያኔዎች ምክንያትን እየፈጠሩ ወጣቱን በግፍ በመግደልና በማሰር ትውልዱ በፍርሀት እንዲርድና ከትግል ራሱን እንዲያገል ለማድረግ እና የራሳቸውን የስልጣን ዘመን ቋይታቸውን ማስረዘሚያ አማራጭ መንገድ ማሰር፣ መግደል እና ሕዝብን ማወከብ ነው ብለው ያምናሉ::

ለዚህም ነው ማንኛውም የሰላማዊ ትግል እንቅስቃሴዎች እንዳይሳኩ እና ሕዝብ ተሳትፎ እና እንቅስቃሴ እንዳያደርግ ወያኔዎች ሕዝብን የሚያዋክቡት እና የሚያስሩት ሰሞኑንም የባህር ዳሩ የተቃውሙ ሰልፍ በሚገባ እንዳይካሄድ እና ሕዝቡም ወጥቶ በሰልፉ ላይ እንዳይገኝ ለማድረግ የወያኔ ካድሬዎች እና የወያኔ ቅጥረኛ ፖሊሶች የባህር ዳር ከተማን ሕዝብ ሲያስፈራሩ፣ ሲረብሹ እና ሲያውኩ እንደነበር መረጃዎች ጠቁመዋል :: ነገር ግን የወያኔ ወከባ ያልረበሸው የበባህር ዳር ከተማ የሚኖረው የአማራው ሕዝብ ፍርሃትን በመስበር የኢትዮጵያን ስም እየጠራ እና እያወደሰ ዘረኛውን እና አንባገነኑን ፋሽስቱን የወያኔን ኢአዲግን መንግስት እና ባለስልጣናቶችን በድፍረት ሲያወግዝ እና ሲያዋርዳቸው ማየት በቂ እና ኩራት ነው እያልኩኝ ለባህር ዳር ከተማና በአካባቢው ለሚኖረው ሕዝብ ምስጋናዪን አቀርባለው :: በባህር ዳር ከተማ የተደረገውን እልህ እና ወኔ የተሞላበትን አጠር ያለች የተቃውሞ ሰልፍ ቪዲዮ ይመልከቱ :


የመስጊድ ኢማሞች የሚሾሙት በመንግስት በራሱ መሆኑን መንግስት አመነ!!!

$
0
0

ሕዝቡ ሳያውቀው ሕገ መንግስቱ ተቀይሮ ይሆን?

መንግስት ‹‹እኔ በሾምኳቸው የመስጊድ ኢማሞች (አሰጋጆች) አልሰገዳችሁም›› በሚል ንጹሀን ሙስሊም ግለሰቦች ላይ ክስ ያቀረበበት ሰነድ ተገኘ!!!
ከፍርድ ቤት የውስጥ ምንጮቻችን የተገኘውና በፌደራል አቃቤ ህግ አቶ ብርሀን አለባቸው ፊርማ በታህሳስ 4/2006 የተጻፈው ይኸው የክስ ሰነድ ለፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አዲስ ከተማ ምድብ የቀረበ ሲሆን ሁለት መስጂድ ውስጥ በኢማምነት ያሰገዱ ሙስሊም ግለሰቦችንም ተከሳሽ አድርጎ አቅርቧል፡፡
muslim

ሰነዱ እጅግ አስገራሚውን ክስ ሲያብራራ አንደኛና ሁለተኛ ተከሳሽ በቁባ መስጂድ የአህባሽ ተከታዩን ኢማም ተከትሎ ለመስገድ ፍቃደኛ ያልሆነውን ህዝበ ሙስሊም ማሰገዳቸውንና በዚህ ተግባራቸውም ‹‹የሃይማኖት ሰላም ስሜት›› መንካታቸውን ገልጿል፡፡ ቃል በቃልም ሁለተኛ ተከሳሽ ‹‹መንግስት በሾመው ኢማም ቦታ ላይ በመቆም ሳይፈቀድለት የእነሱን ተከታዮች በማሰገድ ሰላማዊው ሙስሊም እንዳይሰግድ በማድረግ…›› ወንጀል መስራቱን ገልጿል፡፡
እስካሁን ‹‹መንግስት በሃይማኖት ጣልቃ አይገባም የሚለውን ህገ መንግስታዊ መርህ አልጣስኩም›› እያለ ሲከራከር የቆየው መንግስት በተለያዩ አጋጣሚዎች ሲጋለጥ የቆየ መሆኑ የሚታወስ ሲሆን አሁን ግን መከራከሩ እንደማያዋጣው አውቆ በማን አለብኝነት ‹‹እኔ የሾምኩትን ኢማም አልተከተላችሁም›› በሚል ፍርድ ቤት ችሎት ማሰየም መጀመሩ ‹‹ህገ መንግስቱ አንድ ቀን ይከበር ይሆናል›› ለሚሉ ወገኖች ትልቅ መርዶ ይዞ መጥቷል፡፡ የአገሪቱ ‹‹የፍትህ›› አካላት የሆኑት ዳኞች እና አቃቤ ህጎች መንግስት የሾመውን ኢማም ተከትላችሁ አልሰገዳችሁም›› በሚል ኢ-ህገ መንግስታዊ ክስ ላይ በይፋ መሰየማቸውም ለሀገሪቱ የፍትህ ስርአት የቁልቁለት አዘቅት መሆኑ አያጠራጥርም!
ህዝበ ሙስሊሙ ከ1987 ጀምሮ በመንግስት ሹመኞች ቁጥጥር ስር የዋለውን መጅሊስ ተቀባይነት የነሳውና ለመሪ ተቋሙ መመለስም እስካሁን እየታገለ ያለው መጅሊሱ የመንግስት ካድሬዎች መጫወቻ በመሆኑ እንደሆነ የሚታወቅ ሲሆን በመጅሊሱ ስም የሚካሄዱት ሁሉም ተግባራት በመንግስት የሚሾፈሩ መሆናቸውም የአደባባይ ምስጢር ሆኖ ቆይቷል፡፡ የዛሬውን ዜና ልዩ የሚያደርገው ግን መንግስት ‹‹ሽብርተኝነት›› እና ሌሎች የማስመሰያ ስሞች ሳያስፈልጉት ‹‹እኔ የመረጥኩልህን እምነት አልተከተልክም፤ እኔ በሾምኩልህ ኢማም አልሰገድክም›› ሲል በግልጽ በሰነድ ጭምር ምስክር ጠርቶ ችሎት ፊት ሰዎችን ማቆሙ ነው፡፡ ይህም ይፋ መውጣቱ መንግስት የደረሰበትን የሃይማኖታዊ አፈና ደረጃ ለመላው ዓለምና ለሰብአዊ መብት ተከራካሪ ተቋማት ይበልጥ ይፋ የሚያደርግ መሆኑ አያጠራጥርም፡፡
አዎን! የመንግስት ሃይማኖታዊ ጭቆና በምንም መልኩ መደበቅ የማይችልበት ደረጃ ላይ ደርሷል፡፡ ይህ ግን ከሁለት አመታት በላይ ኢ-ፍትሀዊነትን ሲታገል የቆየው ህዝበ ሙስሊም የበለጠ በትግሉ ላይ እንዲጠናከር የሚያደርገው እንጂ ተስፋ የሚያስቆርጠው አይደለም፤ ህዝብ ተስፋ አይቆርጥም! ህዝበ ሙስሊሙ የሃይማኖት ነጻነቱ እስኪከበርና የዜግነት መብቱን የሚጋፉ አሰራሮች እስኪቀረፉ ድረስ በጽናት መታገሉን ይቀጥላል፤ ድልም ከአላህ እንጂ ከሌላ አይደለምና!!!
ድምጻችን ይሰማ!
አላሁ አክበር!

የቅኔው ንጉሥ ፈላስፋ –የትውልድ ግሥ፤ የኑሮ ስዋሰዋዊ –ምዕት፤ (የሎሬት ጸጋዬ ገ/መድህን ሙት ዓመት መታሰቢያ)

$
0
0

ከሥርጉተ ሥላሴ 25.02.2013 (ሲወዘርላንድ – ዙሪክ)

(„ጥበብ ቤቷን ሠራች፣ ሰባቱን ምሰሶ አቆመች። ምሳሌ፤ ምዕራፍ 9 ቁጥር 1“)

ተግቶ ንጋትን ሠራት። በቀንበጥነት በዝግጁነት ሰማያዊ ጥሪን ታጥቆ ተቀበለ – ጀግና። የማያልቅ ሙቅ ሥነ – ጥበባዊ ስሜትን በተስፋ ስንቅነት ቀመረ፣ አንጥሮ በቅንነት ለገሰ፣ አንቆጠቆጠም። በስብዕናዎቹ ውስጥ ማንነቱን ሰንደቁ ያደረገ ጉልቶ የሚታይ የትውልድ ጌጠኛ ዓውራ። ተግባሩ ዋጋቸው ለዘመናት ሳይቀንስ እዬፈኩ – እዬደመቁ ከሩቅም ከቅርብ በቋሚነት የሚጠሩ ዘላቂ ማገሮች ናቸው። ሃብትነቱ – ሁለመና ሁለአቀፋዊ ሞዴል መሆኑ ብቻ ሳይሆን ዳኝነቱ ጥልቅ ሥልጡን ውስጠ አዋቂ – መርማሪዎች ናቸው። የአፍሪካ ዋርካ፤ የፓን አፍሪካኒስትነት ጠበቃ፤ የሰብዕዊነት ዕጬጌ ነው የቅኔው ዐፄ ብላቴ ጌታ ሎሬት ጸጋዬ ገብረመድህን! ሥጦታ! ምርቃት!
New Picture (4)

ቅኔው – ተዘረፈ
እቶኑም – አጠና …
ቅኔውም አፈራ፤
አብነት – ተጉዞ
ረጅም – ተመዞ
ቅኝተ – መዘዞ፤
ሀቅን – ጎዘጎዘ
ሚስጥርን አፈሰ።
ፈልነን – አፍልቶ
ትናንትን – ፈወሰ።
ዛሬን – አነገሠ …
ሥጦታ – አቀሰሰ።

ግሡ – ተገሰሰ፤
ዜማ ተንተራሰ
ጥበብ – ገሰገሰ።
መምህሩ ነገሠ፤
ድንቅነት – ለበሰ።
በዐለም አንደበት
ሎሬት – ተወደሰ!
ብዕርህ ወተት ናት፤ — ዕልፍን የፈጠረች
መንፈስህ ቅዱስ ናት፤ — ነገን የወለደች
ቃልህም ምህረት ነው፤ — መድህን የቀለበ
ትንቢትህ ዕውነት ነው፤ — ህይወት ያቀበለ
ዓለምን የዳኘ ግኘት – ያበቀለ።
ጥረትህ ዕንቁ ነው፤ – ጸጋን ያፈለቀ
ጨለማን ቆልፎ —- ፍካት ያስደመመ፤
ጸጋህ መድህን ነበር፤ — ጸሐይ የፈረመ።
ሊቅነትህ ቀንዲል – ልቅናህ ገረመው
ፈጠራህ ልዑቅ ነው፤ — ግርማ የነበረው።
ውድም አባት ነበርክ ሳትደክም የተጋህ
ትውፊትን ገንብተህ – ዘመንን የሠራህ።
New Picture (5)
እኔ ትቢያ ለዕውቁ ሁለገብ ፈላስፋ ለመጻፍ አቅሙ የለኝም – ብናኝ ግርድ ነኝና። ፍቅሩን አስቤ ሙት ዓመቱን የካቲት 18ትን ለማጠዬቅ እንጂ። የዲታው የአማርኛ ቋንቋ …. ውብ ቃላቶች ሆኑ ሳቢ ቅላፄዎች፣ እንዲሁም ጹዑም ፍሰቶች ሁሉ ቢቀመሩ ብቃቱን፣ አቅሙን፣ ችሎታውን፣ ጸጋውን፣ ተሰጥዖውን፣ ተንባይነቱን፤ ስበቱን፣ የተመረጠና የሰጠም መሆኑን የመናገር ኩነታቸው ያጠራጥረኛል። …. እሱ ልዩ – ተፈጥሮው ልዩ፣ ውስጡ ልዩ – ቅኝቱ ልዩ፣ ስምንትዮሽ ቤቱ – ጥበብ ግንብነቱ – ፍጹም ልዩ ያደርገዋል። ከጃፓኖች ሃይኩ፤ ከእንግሊዞች ሶኔት፤ ከጀርመኖች – ከኦስትራሾችና ከሲዊዞች ሌይሪክ ከእኛም የወል ቤት የተለዩ የሥነ ግጥም ዬግማድ መሰረት ነው። ቋንቋዎች ሁሉ ጸጋዬ ቤት መስቀላቸው ናቸው። የሥርዬት ድርና ማግ ዘላለማዊ ምጥቅ ብሩክ ….
ወይ ይህቺ አንቦ እንዴት የተባረክች ቅዱስ ቦታ ናት። የሰላሙ አባት የክቡር ማንዴላን ህይወት የታደገው ሚስጢር የሻንበል ጉታ ዲንቃም እትብት። ፈላስፋው ብላቴ ሎሬት ጸጋዬንም የሸለመችን – ጸጋውን በመድህን ጠልፋ በትጋት ባጋቱ ጋቶቿ የቀለበችን – የማትጠገብ ባዕት። ብቁ የእናት መቀነት ልዩ ዳኛ አንቦ።
የደም ገንቦ – አንቦ ጀግና
ቃል ዋና
የተግባር ገናና
የእማ ወዘና
ሥነ – ጥበብን ከነሙሉ አካሉና አቅሙ ወልዶ ዬሰጠ አንቦ – አንባ። ረ/ፕሮፌሰር ብላቴ ሎሬት ጸጋዬ ገብረ መድህን በፎለቄዋ ቦዳ በአምቦ ደቡባዊ ምዕራብ 30 ኪሎሜትር ርቀት ላይ በምትገኘው የጅባትና ሜጫ ግርማን በተላበሰች ገጠር ተራራማ ቦታ ከተከበሩ ክቡር አባቱ ከአቶ ገብረመድህን ሮባ ቀዌሳና ከተከበሩ ክብርት እናቱ ከወ/ሮ ፈለቀች ዳኜ በወርኃ ዬካቲት ወር 1929 ዓ.ም ተወለደ። አንደኛ ደረጃ ትምህርቱን በአምቦ ማዕረገ ሕይወት ቀኃሥ ትምህርት ቤት ከዚያም ሁለተኛ ደራጃ ትምህርቱን ጄኒራል ዊንጌት በመማር ላይ እንዳለ የንግድ ሥራ ኮሌጅ ተልዕኮውን አህዱ ሲል በዛው ትምህርቱን ቀጥሎ በወርቅ ሽልማትና በሚያስመካ ውጤት በማዕረግ ተመርቋል። በኋላም በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዩንቨርስቲ ቤተመጻህፍት እዬሰራ ሳለ አሜሪካን ቺካጎ ኤሊኖይ ወስጥ ከሚገኘው ብላክስቶች ስኩል ኦፍ ለው በህግ ሙያ በተልዕኮ ተምሮ ዲግሪውን አግኝቷል። ከሰማዩ ድግሪ ግን አቻ የሚሆን አይደለም። ያው በስወ – ሰውኛው ስናስበው … በቀለሙም ቢሆን ገፍቶ የሄደ ስለመሆኑ ለማጠዬቅ እንጂ።

የቅኔው ልዑል አውራና መምህር ብላቴ ጌታ ሎሬዬት ጸጋዬ ገ/መድህን በተጨማሪም ከዩኒስኮ ባገኘው ነፃ የትምህርት ዕድል በሼክስፒር የላቀ የትውና -ጥብብ አንባ ወደ ሆነው እንግሊዝ ሀገር ሄዶ Royal court Theatre፤ ፈረንሳይ Comedian Francaise፤ በኢጣሊያን ሀገር ደግሞ Opera መድረኮችን እዬጎበኘ የተውኔትን ጥበባትን አጥንቶ ተመልሷል። ይህ ወቅት ኢትዮጵያን በውስጡ እስቀምጦ በሥነ – ተውኔት ዘርፍ እኩል ደረጃ እንድታገኝ ኃላፊነቱን በቅንነት ወስዶ እናቱን ወደ ፊት እጅግ በበቃ ችሎታ ለማራመድ በመንፈሱ ውል ያሰረበት ነበር ማለት ይቻላል። ምክንያቱም በህይወት ዘመኑ ሁሉ የከወናቸው አይነታ ተግባራት የኪዳኑ ወርቃማ ማህተም ናቸውና።። በዘርፉ በመሪነት ኢትዮጵያን በእኩልነት ተርታ ትሰለፍ ዘንድ ታድጓታል። ፊት ለፊትም አምጥቷታል። በጸጋው ፍሬ ጠቀስ ጉልበት ኃይልና አቅም ፈጥሮላታል። አንቱነቷን በውስጥነት አፍልቆታል – አጸድቆታል።

የጋሼ ጸጋዬ ጥረት በመሆን የከበረ፤ በድርጊት የበለጸገ ስለሆነ ውለታውን ለመክፈል አድናቂዎቹ ሆነ አክባሪዎቹ ይህን የሚመጥን አቅም የለንም። ቀድሞ ነገር አልጀመርነውም። ፈርተነዋል። እንሆ ጊዜ ገቢረ ለእግዚአብሄር ነውና ሥነ – ጥበብ ፈልጋው ከሰማ ሰማያት ወርዳ ወደ ሳቂተኛዋ ቦዳ ተጉዛ ብላቴናውን ልጇን በቅዱስ መንፈስ ኃይል መረጠች። ውስጧ ሆኖ የልጅነት ጊዜውን ተጠበበባት። በወተቷም አድጎ በለጸገባት። በማህጸኗ ፍልስፍናን አዳጎሰባት። በህሊናዋ ማህደር ሆኖም ዛሬንና ነገን በቋሚነት አንፆ ሥነ ጥበብን ልዕለ – ሐሴት ብሎ ሰዬማት። ትውፊትን ሰርቶ በዘላቂነት በባለቤትንት እኛን ትሆን፤ ትመስልም ዘንድ፤ መከራችን፣ አሳራችን፣ ደስታ ፍሰኃችን ፈቅዳ ትጋራንም ዘንድ ሸለመን።
New Picture (6)
ዓራት ዓይናማው ፈለገ ህይወትም የአንደኛ ደረጃ ት/ቤትም ድልድይን አመሳጠረች። „ የሁለቱ ባህሎች ውጤት አካል ሆኜ ነው ያደኩት። ድልድይ ሆንኩኝ። አፍ የፈታሁት በኦሮምኛ፤ እርባታ የጀመርኩት ደግሞ የግዕዝ ግስ በመግሰስ ነበር“ ብሎ ሚስጢሩን ፈልቀቅ አድርጎ ያቃመሰን የቅኔው ልዑል ብላቴ ሎሬት ጸጋዬ ገ/መድህን በሊጋባነቱ ተዝቆ በማያልቀው ዕውቅ የሊቃናት መንደር ልቅናውን ነፍስ የሰጠው፣ መክሊታዊ እስትንፋሱን ከቅዱስ መንፈስ ጋር በመስተጋብር ያዋኸደው በእናት አባቱ እልፍኝ ሥር ይልቁንም በእናቱ ወገኖች በነ አለቃ ማዕምር ዳዊት የመድገምና የቅኔ ግሥ የመግሰስ፤ ድንጋጌዎችንም የመቀለብ ቡቃያ እድል በማግኘቱ እሱም የትውልዱ የግሥ እሸትና ፍሬ እንዲሆን ምርጥኑቱን አትሞበታል። ድልድይነቱም የምህረት አባት፣ የፍቅር አብነት፣ የአብሮነት ጉልላት መሆኑን በብርኃናማ ድርጊቶቹ ያመሳጠረ „የተራራው ስብከት“ በመሆኑ ከትውልድ ወደ ትውልድ በትንግርትነት ይዘልቃሉ።

ዘመናዊ ትምህርቱን በአምቦ ማዕረግ ህይወት የመጀመሪያ ደረጃ ት/ቤት የጀመረው ብላቴናው ጸጋዬ እንደ ባለቅኔው፤ ከእረኝነት እንደ ተመረጠው፤ ፈጣሪ አምላካችን መዳህኒተዓለም ክርስቶስ እንደ ልቤ እንደ አለው እንደ ንጉሥ ዳዊት ብላቴ ጸጋዬም በጥቁር መሬት የአፍሪካ የሥነ ጥበብ ሙሴና ብቁ ዕንቁ፤ እንዲሁም ተመራማሪ እንዲሆን የልቅና ማዕረግ የተሰጠው ገና በ13 ዓመቱ ነበር። ታምሩም በበኽሩ ቲያትሩ „የዲናስዮስ ዳኝነት“ በ1942 ዓ.ም አዲስ ምዕራፍነቱን ፏ ፍንትው አድርጎ በምልክትነት ተከፈተ።
New Picture (7)
ዕድለኛው ብላቴና ይህን ፍጹም ልዩ ጸጋ ቀምሞ፣ አንጥሮ፣ አብስሎ፣ አስመችቶ እንዲይዝ በሩን ቧ አድርጎ የከፈተለት ሌላው ወርቅ አጋጣሚ ደግሞ እሱም እንዳለው ከሁለቱም ታላላቅ ማህበረሰቦች ባህልና ወግ፤ ልማድና የህይወት ተመክሮ መብቀሉ፤ ቀለማም ውበቱ ዲካ የለሽ እንዲሆን አድርጎታል። ጋሼ ጸጋዬ ቀለም ነው – የማያልቅ። ጋሼ ጸጋዬ ጥበብ ነው የማይነፍስበት። ጋሼ ጸጋዬ ሰዋሰዋሰው ነው ያልተተበተበ። ጋሼ ጸጋዬ ሐረግ ነው – የሥርዐት፤ ጋሼ ጸጋዬ የእናት ኢትዮጵያ፣ የአፍሪካ፣ የዓለም የጥበብ አውደ ምህረት ነው – ክብር የሆነ ቅኔ ዘጉባኤ። የጋሼ ጸጋዬ አንዱ ነጠላ ሥራ … ቃናዊ ሀገር ነው። አንዱ ነጠላ ካራክተር የአንድ ትውልድን የኑሮ ዘይቤ ጌጣማ አድርጎ ያብራራል – ያወራርሳልም። አንዱ ዘለላ ንዑስ እርስ – የፊደል ገበታ ነው። ጥቅሉ ሲሰላ ለሺህ ዘመናት ማውጫ ነው። ጋሼ ጸጋዬ ሲተረጎም ሰንደቅዓላማችን ነው – ለሥርጉተና ሃሳቡን ለሚጋሩት።

የፋክት ውበት በብላቴ መንፈስ ይገለጻል …. ትንቢትም ቢሆን በሎሬት ህሊና ተለክቷል „ሰቆቃው ጴጥሮስ“ ትናንትን ከዛሬ፤ ዛሬን – ከነገ አጋብቶ ይመሰክራል፣ ታሪክ ከትንሹ እሰከ በኽሩ የነፃነት ገድል በሃቅ ድባብ ተቀኝቶታል፤ ለመሆኑ አፍሪካን ነፃ ያወጣውን ገድል እንዴት ዘከረው … ንጉሡ ባለቅኔው። ከተቃኜው የማስተዋል ፍሬዎች ለማገናኛ ድልድይነት የተጠቀመበትን ብቻ በጥቂቱ ….

„ዋ አንቺ ዐድዋ ….“
„.. ዐድዋ የዘረ ዐፅም ርስትዋ
የደም ትቢያ መቀነትዋ
በሞት ከባርነት ሥርዬት
በደም ለነፃነት ስለት
አበው የተሰውብሽ ለት
ዓደዋ …
የኩሩ ትውልድ ቅርስዋ
የኢትዮጵያ ምስክርዋ
ዓድው“ (የካቲት 1964 ዓ.ም ዓድዋ)
ለእናት ሀገሩ ያለው ፍጹም ሊለካ የማይችል ፍቅርና ክብር ህይወቱን መሉ አንዲትም ሰከንድ ሳያስተጓጉል በታማኝነት አደግድጎ፤ በሎሌነት ፈቅዶ፤ እራሱን በቀጥታ ሰጥቶ አግልግሏታል። ከጋሼ ጸጋዬ የመንፈስ ማህጸን ውስጥ እናት ሀገሩ ኢትዮጵያ ዘውዷን ደፍታ አለች። … ወደ ለንደን ጎራ ባላበት ጊዜ ፍቅሯ፣ ናፍቆቷና ስስቷ አላሰቀምጥ አላስቆም ሲለው፤ ፋታ ነስቶ ሲያስጨንቀው፤ መንፈሱን ሲያባትለው፣ ሲታገለው፤ ከውብ እቅፏ መራቁን አልችለው አለና ናፍቆቱን እያበባለ፣ ፍቅሯን እያደመጠ፣ ጸጋዋን ሲጨልጥ፤ የውስጡን የናፍቆት ዕንባ እዬለቀቀ ሰቀቀናዊ – ስስታዊ – ስሜታዊ ውስጡን በተመስጦ እዬተረጎመ …. ሁለመናዋን ጥልቅ በሆነ ፍጹም ሊገለጽ በማይችል የናፍቆት ረመጥ ላይ ሆኖ እንዲህ ይላታል እናቱን … በጥቂቱ … እናንተ ዝለቁት የማከብራችሁ።
ደህና ዋይ እማማ

„ …. እናት አለም የስሜ አርማ
የህይወቴ ወዝ የይኔ ማማ
እማትነፍጊ እማታቅማሚ
እማታሳጪ እማታሚ

እኔን በራበኝ በጠማኝ አብረሽኝ እምትጠሚ
ጥቃቴን እምትጠቂ ቁስሌን እምትታመሚ
ፍሰሃዬን፣ ፈገግታዬ ሳቄን ብቻ እምትፈልጊ
አንቺ እማማ
አንቺ የነፈሴ ልብ ዓልማ
የይኔ ማማ (ሎንደን 1953)

ረ/ፕሮፌሰር ብላቴ ጌታ ሎሬት ጸጋዬ ገ/መድህን የእናቱን – ውላታውንም በሚገባ የመለሰ ብርቅ ጠንቃቃ ልጇ በመሆኑ እሱን መሰል ልጅ ደግማ ለማግኘት እናት ኢትዮጵያ 200 ዓመት መጠብቅ ግድ ይላታል …. ። ለዛውም ከተሳካላት ብቻ። ሰቆቃው ጴጥሮስ ላይም ስለ እናቱ የቋጠረውን … መመልከት እንችላለን። በነገራችን ላይ …. ጋሼ ጸጋዬ
ትንቢት ራዕይ ይታዬው ነበር እንደ ንጉሥ ዳዊት ….. የሥነ ጥበብ ንጉሡ ብላቴ ጌታ ሰቆቃው ጴጥሮስ ሙሉውን ተመልከቱት። እርግጥ ነው ደራሲ ምስባክ ወርቁም „ዴርቶ ጋዳን“ የጸፉበት ጭብጥ ነው ረቂቅ ሥራ …. ከሰሞናቱም ከዚህ ረቂቃዊ ትንቢት ጋር የሚጋባ ከመጸሐፉ ታሪክ መነሻ መቼትና ልቦና ላይ የተነሳ የወርቅ እንክብል እያዬን ነው። መድህንና መድህን ሲገጣጠም – በትንቢት ሥነ -ግጥም። ምዕራፉን በግልብ ሳይሆን በማስተዋል ሆነን መንፈስ ቅዱስ እንዲገልጽልን ከልብ ጠይቀን እንመርምረው በአንክሮ – በተደሞ። ትናንት ገባ ሁዳዴ – የጸና መንፈሰ – ሱባኤ ….

„አዋጅ የምሥራች ብዬ የትብት ምግቤን ገድፌ
ከናቴ ማኅጸን አርፌ
ካፈርዋ አጥንቴን ቀፍፌ
ደሜን ከደሟ አጠንፍፌ
ከወዟ ወዜን ቀፍፌ …“ (1961 ቀበና?)
ሌላው አህጉራዊ ግንዛቤውና ፍቅሩ ሚዛንነቱን ያዘክራሉ፤ ብላቴው ተፈጥሮው የተሰበሰበ ህብርትን በሚዛንነት ይገልፃል። ዘልቆ ረጅም ተጎዞ ሚስጢራትን ይቀድማል። የወጣላት የመሆን ሻንፒዮን። ዩኒስኮ ለመጀመሪያ ጊዜ አዘጋጅቶት በነበረው የጥቁሮች ፌስቲባል ላይ ዳካር ሴኒጋል፤ የፓን አፍሪካ ፌስቲባል አልጀሪያ ላይ ተገኝቶ ሀገራችን ኢትዮጵያን ከፍ ያለ ክብር አሰጥቷታል። የልቧናው ህሊና መጎናጻፊያው እናት ሀገሩ ዘንካቲት ኢትዮጵያ ናትና። የደም ዝውውሩ ሂደት ጤናማነት ጥበቃው ለእናቱ ከአለው ታማኝነትና ፍቅር መፍለቁን የተሰጠው ነውና አድርጎታል። ጥበቃው ማህሏ፣ ዳር ድንበሯ ትርፋማነቱን በማህበራዊነት አጋርቶናል። ዘብ የቆመላት ዘብ አደሯም ነበር። ቅጥር ደንበሯን አስጠባቂ። በዓይኗ ብቻ ትእዛዟን እዬተከተለ የሚከውን ንቁ አሥራቷ።

ረ/ፕሮፌሰር ብላቴ ጌታ ሎሬት ጸጋዬ ገ/መድህን ለእኔ ምዕተ ዐመት ነው። ፍጥረተ ነገሩ ለዬት ብሎ፤ ዘለግ ብሎ የተሰጠው ፍጹም እቅፍ ሙሉ ሽልማታችን ነው። ጋሼ ጸጋዬ የእርቅ ድልድይም ነው። ሳይሳሳ ውስጡን የሰጠ በመሆኑ እነሆ በውስጣችን ተደላድሎ መቀመጥ የቻለ የፍቅር ታላቅ ሐዋርያ ሀውልታችን ነው። ጋሼ ጸጋዬ የባህል፤ የታሪክ፤ የሥነ – ጹሑፍ፤ የተውኔት፤ የአስተዳደር፤ የቅኔ፤ የብቁ ዲፕሎማሲያዊ ጳጳስ፤ የገንቢ ትችት አፍላቂ – ዩንቨርስቲ ነው። ብላቴ እራሱኑ ሆኖ ኖሮ፤ እራሱን ሰጥቶ፤ ምንም ሳይቆጥብ ኢትዮጵያን በዘመናዊ የሥነ ጥበብ ዋልታ ብቁ እንድትሆን ብድግ ያደረገ የሰው ስው ነው። የተውኔት ጌታው ሰማያዊ ጥሪውን በተግባር ያሰበለ ትውልድ ከቶውንም ሊተካው የማይችል ዘረ – ቅኔ ነው። አዲስ የሥነ ጥበብ ትውልድን አምጦና አመሳጥሮ በመንፈስም በተግባርም የወለደ የዕውነት ዙፋን ነው። ጠረኑ የትውፊት ስንቅ ቅርስም ነው።

የቅኔው ልዑል አፍሪካን በኸረ የሥነ – ጥበብ ማዕከል እንድትሆን ያደረገ የተግባር አዝመራ ነው። የአፍሪካ የሥነ – ጥበብ ብሩክ ርትዑ አንደበት። ብላቴ ጌታ የቋንቋ ቃና ሥልጡን ፈላስፋና ተመራማሪ ነው። ነበር ማለት ይከብደኛል። ስለምን? የሥነ ጥበብ አድባር በጠራችን ቁጥር እሱ አለና። እንዲያውም ለእኔ ጋሼ ጸጋዬን እምተረጉመው እጅግ በበዙ ሙያዎች ብቃቱ ሙሉዑ የሆነው ጣሊያናዊ ታላቅ ሳይንቲስት ከሚዚያ 15. 1452 እስከ ግንቦት 2.1519 ለዘመኑ ሳይሆን ለ30ኛው ምዕተ -ዓመት ተፈጥሮ የነበረው ድንቅ ሊወናርዶ ዳንቤቺ ከሠራቸው ዕጹብ ሥራዎች ውስጥ አዳም ከመዳህኒታችን እዬሱስ ክርስቶስ መንፈሱን ሲቀበል ፍጹም በረቀቀ ሁኔታ በመንፈስ ቅዱስ ተመርቶ የቆረበበትን ጣታዊ ንክኪ ተግባሩን ሳስብ በዛ ውስጥ ለዬት ብለው ከተፈጠሩትን አንዱ የእኛው የቅኔው ልዑልን ጋሼ ጸጋዬን እንደሆነ ነው እማነበው።
ብላቴ ጌታ ሎሬት ጸጋዬ ገመድህን የጥበብ ባለጸጋነቱን ከዚህ አንጻር ነው የማዬው። በዛ የመንፈስ ቅኝት ውስጥ፤ በዛ ርቁቅ ምርቃት ውስጥ ከኢትዮጵያ …. አንድ ብላቴና መመረጡን ሊወናርዶ ዳቤኔቺ አብስሮኛል። ቀድሞ የተናገረው ትንቢት ይፈጸም ዘንድ …. ጋሼ ጸጋዬን ሰጠን እላለሁ እኔ ሥርጉተ ሥላሴ። ስለሆነም ነው ምርጦቹ በሥጋ ተለይተውን ልክ እንደ አሉ ሆነው የሚሰሙን። ነበር እያሉ መጻፍም የሚከብደው ለዚህ ነው። ለሰከንድ በመንፈሴ ውስጥ የኔው ሊቁ ሎሬት የአፍሪካ ቀንዲሉ ጋሼ ጸጋዬ ወጥቶ አያውቅም …. እኔ ስለ እሱ ቀናተኛ ነኝ። ንድፉ መንፈሴን በግልጽነትና በቅንነት ገርቶታል እና … ፍቅሩም ጥልቅ – ዝልቅ።

ጋሼ ጸጋዬ ኢትዮጵያዊነት ሚስጥር ስለመሆኑ ማንነትን በጥልቅ ምርምሩ የገለጸበት „እሳት ወይ አበባ“ መድብሉን አጠቃሎ አንብቦ ለተመረቀበት፤ ከውስጡ ላስቀመጠ ሆነ ድርሳኑ ላደረገ ሰብዕ ማንነቱን አውቆ እራሱን እንዲያከብር ፤ ማንነቱንም እንዲከበክብ – እንዲወደውም ያደርገዋል፤ ለአራት ዓይናማው ለሊቀ – ሊቃውንቱ ለብላቴ ጸጋዬ ገ/መድህን ኢትዮጵያ የፍጥረታት ጭማቂ ንጥር ርስት ስለመሆኗ በትጋት ሰብኳል፤ የአብነት መምህር ሆኖ በታታሪነት አስተምሯል፤

ገላጭ ሆኖ ዕውቅናዋን በዓለም ባባተሌነት መስክሯል አስውቧታል – በተግባሩ አድምቋታል። የአፍሪካ አንድነት ድርጅት አህጉራዊ መዝመሩ ግጥሙ ኢትዮጵያ የአፍሪካ አጀንዳ እንድትሆን አድርጓታል። ይህም ብቻ ሳይሆን በመዝሙሩ ቅመም ውስጥ የኢትዮጵያዊነት ሚስጥር ተቀምሞበታል። ተገደን ተቀበልን ለሚሉት መዳህኒቱ እሱ ነው። ታቦቱን ሲከበክባት፣ ሲያነግሥት – ሲያቀሳት – እጬጌነት ሲሾማት – ሲሸልማት – ማድመጥ ለተሰጣቸው መርምሮ ይገለጣል – ሥራዎቹ ያልባለቁ ደናግል ሃኪሞችም ናቸውና – ወደር የለሽ ፈውሶች።

ፈቅጃት ሳታዬኝ ዐመት ቋጠጣረች*(ዘመን ቆጠረች)
ስወዳት እራቀች ….
ስሳሳት ጨከነች
ሳልጠግባት ሾለከች
ስፈልጋት መጣች
ሳምጣት አጠባች
ስንቅም ቋጠጣረች*(መሃያ ሰፈረች፤ ቀለብ ሰፈረች)
በመንፈሴ ብሌን መሰረት ቸከለች።

እላለታለሁ እኔ የአባቴን የወርቅ ቀለጦ ጠብታቱን …. ለጥቄም – ለትጥቄ እንዲህ እላለሁ -

ናፍቆት አፍተልትሎ ሲወቃኝ ሲደቃኝ አንዲሁም ሲለካኝ
አንቆ ሲታገለኝ ትዝታ ሊውጠኝ ሊበላኝ እንዲህ ሲሟገተኝ
ጥልፋማ ብዕርህ በፅናቱ ቃኜኝ
በቃኝ አስተማረኝ፤
ትእግስት ኮለኮለኝ – ተስፋህም ቀለበኝ።

ረ/ፕሮፌሰር ሎሬት ጸጋዬ ገ/መድህን „የእሾህ አክሊልን“ በ20ኛ ዐመቱ ቀጥሎ „በልግን“ „የደም እዝመራን“ ተውኔቶችን ለህዝብ በማሳዬት ለዘመኑ እጅግ የቀደሙ ሥራዎቹ ባለተሰጥዖነቱን ስለ አወጁ በ29 ዓመቱ የቀዳማዊ ኃይለሥላሴን ሽልማት በሥነ – ጹሑፍ ተሸልሟል። በተለያዩ አለምአቀፍ መድረኮችም ተወድሷል – ተሸልሟል። የጋሼ ጸጋዬ የሥራና የህይወት ተመክሮ ጥልቅ ከመሆን አልፎ ትጋቱና ጥንካሬውን እኛን እንድንታዘብ አዘውትሮ በትህትና ያስተምራል። ስለሆነም … በቅኔው ንጉሥ የባከነች አንዲትም ደቂቃ አልነበረችም። ዝቀሽ የሆነ ገቢራዊ ነበርና። ትንታግ! ስለሆነም ….

- ከ1957 1963 ዐ.ም በቀ.ኃ.ሥ ቲያትር አርቲስቲክ ዳሪክተርነት በ164 ዓ.ም የ ኦክስፎርድ ዩንቨርስቲ ፕሬስ የአዲስ አበባ ቢሮ
- በ1964 – 1968 በባህልና ስፖርት እስክ ምክትል ሚኒስተርነት ማዕረግ አገልግሏል።
- በ1969 ዓ.ም በአዲስ አበባ ዩነቨርስቲ የትምህርት ክፈል በረዳት ፕ/ ማዕረግ የዩንቨርስቲው የቲያትር የትምህርት ክፍል በመመሥረት ዲያሪክተር በመሆን በአዲስ ግኝት ተውኔትን ተንከባክቦ ዘርቶ፣ አብቅሎ፣ አስብሏል።
- ከ1949 – 1969 አያሌ ተውኔቶችንና ሥነ ግጥሞችን በማያቋርጥ መክሊቱ በገፍ ያመረተው የቅኔው ንጉሥ ከዓለም ሥነ ጥበብ ሃብቶች የሚያድንቃቸውን ከሼክስፔር ሥራዎች እነኦቴሎን ሃምሌትን ወዘተ …. እና የሌሎችንም ወዳጆቹን ሥራዎች ወደ አማርኛ በመተርጎም የተዋጠለት የተግባር ጉልበታም ካስማ ጥሏል። እንግሊዘኛ ተውኔቶችን ግጥሞችን ጭምር በመድረስና ለመድረክ ዕውቅና በማብቃት ዓለም ዓቅፍ ድንቅነትንና ዕውቅናን አትርፏል። በብላቴ ጌታ ጸጋዬ ምግባራዊ እንቅስቃሴ ወስጥ ሁሉ ደግሞ እናት ሀገራችን ኢትዮጵያና የክብሯ መግለጫ ሰንደቅዓላማዋ፤ የህዝቧ ቀለማም ሥነ – ተፈጥሮ ሁሉ የሥነ ጥበብ ታላቅ ብቁ ባለማዕረግ፣ ባለ ሙሉ ሥልጣን አንባሰደር ነበሩ ማለትም ይቻላል። ዕውደቱ ሁለገብና ትርፋማ ነውና።

ጋሼ ጸጋዬ በቀንበጥነት ዕድሜው፣ ከእሳት ውሃ በሚባልበት አፍላ የኩብልና ወቅቱ የሥነ -ጥበብን ሰማያዊ አደራዊ ጥሪን ተቀብሎ ኃላፊነቱን ለመወጣት ባገዙት ጉዞወቹ በ26 ዓመት ዕድሜው ወደ 30 ያህል ሀገሮችን እንደ ጎበኜ ባዮግራፊውን የጻፉት ሊቃናት ይገልጻሉ። በተጨማሪም በአፍሪካ ጥቁር ህዝቦች ባህልና ሥነ – ጥበባት ምርምሩ ፈላስማነቱንና ታሪክ ተማራማሪነቱ በአንድምታ ቀደምት ሊቃናት ይመሰክራሉ። ብላቴ ጌታ ሐዋርያው ሎሬት ጸጋዬ የኢትዮጵያ ደራስያን ማህበር፤ የእፍሮ ኤሽያውያን ጸሐፊዎች ማህበር፤ የአፍሪካ አንድንት ድርጅት Think Tank Form አባል ብቻም ሳይሆን የአፍሪካ ጸሐፊዎችና የአፍሪካ ተመራማሪዎች ማህበራት አባል በመሆን ሁለገብ ተሳትፎውን በብቃቱ ከሽኖ እናት ሀገራችን ኢትዮጵያ የፈካች – ብቁ – ተናፋቂ ማዕደኛ እንድትሆን አድርጓታል። አንባሳደርነቱም ከተለመደው በላይ የታሪካችን ባለፈርጥ ማህደር ነው።

የቅኔው ልዑል የዐለም ዐቅፍ ባለ ቅኔዎች ሎሬቶች ኅብረት አባል ስለነበር በዬአንዳንዱ ሥናዊ አጋጣሚ ሁሉ እናት ሀገሩን ኢትዮጵያንና ምክሊቱን ከፍ ለማደረግ ተጋድሎ እንደ ፈጸመ ይሳማሙበታል ዓራት ዓይናማዎቹ የኛዎቹ ሆኑ የውጭ ሀገር ሊቀ – ሊቃውንታት። … እንግሊዝ ሀገር ኪንግሻዬር የተከናወነው የዓለም ባለቅኔውችና ሎሬቶች ጉባኤ ላይ „ የዘመኑ ድንቅ ባለቅኔ ሲል የወርቅ አክሊል ሸልሞታል። ስለዚህ ኢትዮ – አፍሪካዊውን ብላቴ ጌታ ሎሬት ጸጋዬ ገ/መድህንን ዓለምዓቀፍዊ የጥበብ ሰፊ ማሳ እንደ ዓይኑ ብሌን ይመለከተው የነበረ ታላቅ የብዕር ከዘመኑ በላይ የመጠቀ
ችሎታና ክህሎት የነበረው አርበኛ፣ የሥነ – ቋንቋ ሳይንቲሰት ስለነበር በአሜሪካን ሀገርም የላቀ ሽልማትን በክብር አግኝቷል። ሽልማቱ የማንነታችን አንጸባራቂ አሻራ ነው።

ድምቀት በተሰጥዖ
ፍቅር በተመስጦዖ
ታሪክ ደምቆ ዋለ
ጸጋዬ አዋዋለ
ጽናትን ሰንቆ ምጥን ገላገለ።
ረቂቅነቱ በዓለም ተናኘ
ከድንቅነሽ መንደር መላቅም ተገኘ።
አፍሪካ ደመቀች
ኢትዮጵያ ፈለቀች
መድህን ታሪክ ሰርቶ
ጥበብ ሁሉን ሰቶ
ሎሬትን መረቀ
ውስጥነን አጉልቶ።
ጧፉም – ለዘለአለም
የእምዬ ዓይንአለም።

የቅኔው ንጉሥ የተውኔት ልዑል ዝክረ ብቃቱ በሀገር ውስጥ ሆነ በልዩ ልዩ ዓለም ዐቀፍ መድረኮች የህይወት ታሪኩ ተተንትኗል፤ ለምርምር ተግባርም ውሏል – ለወደፊትም። ሲከወን – ባለቅኔ ሎሬዬት ብላቴን ጌታ ጸጋዬ ገ/መድህንን በተውኔት ዘርፍ ብቻ ሳይሆን ከጻፋቸው 41 ሥራዎች ውስጠ ከተረጎመውና በእንግሊዘኛም ከጻፋቸው ጭምር 12ቱ በሳንሱር ታግደዋል፣ 21 ተቆራርጠዋል፣ 3ቱ ግማሹ ለግማሽ ተሰርዞባታል፣ 4ቱ ድርሰቱን ሳንሱር እንደማይፈቅድለት አይሆኑ ሆኗል።

በሌላ በኩል ከሦስት የሥነ ግጥም መጸሐፍቶቹ ውስጥ 2ቱ ገና አልታተሙም፤ በአንዲት „ጆሮ ገድፍ፡ በምትባል ቲያትር ምክንያት በአፄ ኃይለሥላሴ ዘመነ መንግሥት ወቅት ለ24 ሰዓት በቁጥጥር ሥር ውሏል። በዬዘመኑ በነበሩ የሳንሱር ቢሮዎች በአማርኛ፤ በኦሮምኛ እንዲሁም በእንግሊዘኛ የጋሼ ጸጋዬ ሥራዎቹ ሁሉ ካለማዕቀብ ወጥተው ቢሆን ምን ሀገር ይበቃቸው ነበር?! በውስጣቸው ያያዟቸው ትንቢቶች፣ ትንግርቶች እንዴት ለመንፈስ ፍትኃትን በሰዬመ ነበር?! ባለመታደል አልቻለም እንደተከደኑ በሥጋ አለፈ …. … እጅግ አዝናለሁ። እሱን ያህል ታላቅ የሁለመና አባት ጸጋዬ
ፋውንዴሽን ሳይመሰረት፣ በሥሙ ትምህርት ቤት ወይንም ክሊንክ ወይንም ሙዚዬም ወይንም ዩንቨርስቲ ሳይገነባ ዘመናት አለፉ። ይህ ደምና መግል ማህጸንን የሚያስለቅስ ገመናችን ነው – ሁላችንም ልንጋራው የሚገባው ቁልጭ ያለም ድክመታችን።

የመንፈስ ሰብሎች እጅግ በርካታ ናቸው። ወላዊ ሥራ ወይንም ቲም ወርክ ልዩ መለያው የነበረው ጋሼ ጸጋዬ በግልና በጋራ የሠራቸው … „የዳኒሲዮስ ዳኝነት፤ በልግ፤ የደም አዝመራ፤ እኔምኮ ሰው፤ የእሹህ አክሊል፤ ክራር ሲከር፤ አስቀያሚ ልጃገረድ፤ እኔን ብዬ መጣሁ፤ ቴወድሮስ፤ ሚኒሊክ፤ ጵጥሮስ ያቺን ሰዓት፤ ዘርዓይ ደረስ፤ ጆሮ ደግፍ ገድፍ፤ ሀሁ በስድስት ወር፤ እናት ዓለም ጠኑ፤ መልእክተ ወዛደር፤ አቡጊዳ፤ ጋሞ፤ ሀሁ ወይም ፐፑ፤“
… የምጸት ኮሜዲ አልታዬም፤ ዐጽመ በዬገጹ – በወል ደግሞ ከሊቃናት ባልደረባዎቹ ጋር … „ጸጋዬ ገብረምድህንና ሃይማኖት ዓለሙ „ሰቆቃው ጵጥሮስ ትንሣኤ ሰንደቅ ዓለማ“ ጸጋዬና አባተ መኩሪያ „የመቅደላ ስንብት“ ጸጋዬና ተስፋዬ ገሰሰ „ጥላሁን ግዛው“ ጸጋዬና ገብረክረስቶስ ደስታ „ዐጽም ፈልጉ“ በርካቶቹ ወደ እንግሊዘኛ ተተርጉመው አድናቆት አትርፈውለታል፤ ከላይ ለመግለጽ እንደሞከርኩትም ሳንሱርድ ያነቃቸው የሀቅ ጭብጦች ወደ ታዳሚዎቹ ሳይደርሱ ታዳፍነው በርካቶቹ ቀርተዋል። አንድ ትንሽዬ ተግባር ለመስራት ካራክተር መረጣው፤ ጭብጡን በማደላደል፤ ስሜቱን ወስዶ በማወራረስና በማዋህድ፤ መቼቱ፤ የመድረክ ቅንብሩ አመራሩ ቢሮክራሲው። እንዲሁም ምቀኛው ሸሩና ተንኮሎ ይህን ሁሉ ተቋቁሞ ተውኔትን ፈጥሮ በሁለት እግሯ እንድትቆም አደረጋት ጀግናው። በሁሉም ለህዝብ ዕይታ ዕድል ባገኙት ሥራዎቹ ውስጥ እናት ሀገራችን ውቢት ኢትዮጵያ ዙፋን ላይ ሆና በካባ በተክሊል ተንቆጥቁጣ ትገኛለች። ታድሎ! ምርቃት አስታደለን። ተመርጦ! በፍቅር አስመረጠን። ተከብሮ! በማዕረግ አስከበረን።፡

ጋሼ ጸጋዬ በፈተና ታሽቶ አፍርቷል። በሳንሱር ቢሮ ግልምጫ – ገሳጼ – ዘለፋ – ዛቻ – ግልላ – ወቃሳ ባላበራ ሁኔታ ቢደርስበትም ፈተናዎችን ሁሉ በጽናት ረቶ ለዘለዓለም የማይጠፋ ብርኃንን ያበራ የትናት የዛሬ የነገም ጸሐያችን ነው። እኔ በግሌ እስከ ዕለተ ትንፋሽ እሰምታቆምበት ድረስ ስለ እሱ የምችለውን ሁሉ አደርጋለሁ። ክብሬ – ኩራቴ፤ መጽናኛዬ – መሸሸጊያዬ ብዕሩ ሆነ ምስሉ እራሱ አድህኗዊ ነውና … ለእኔ። ሁለመናው ትውልድን በሰናይ የሚያይዙ ጥበብ ናቸው።
ተው ብለው አይሰማኝ
ልቤ እዬወሰደኝ
ዕንባ ስንቅ ሆኖ እንዲህ ሲፈትሸኝ
ስፈተግ በስደት ስታሽ በሰቀቀን …
አተረፈኝ አሱ ሁሌ ሕይወት ሆነኝ።
የቅኔው ንጉሥ እንደ ዛሬዋ ቀን የካቲት 18 ቀን 1998 ዓ.ም በ69 ዓመቱ አረፈ …… በሥጋ ተለዬን። መንፈሱ ግን ለፈቀድልነት እንሆ ይመራናል። መንገዳችንንም ያሳያናል። ሰውም ፈጥሯል የመጀመሪያዋ የተውኔት ጸሐፊና ብሄራዊ መሪ ለነገም የልቤ መሪ ድንቋን አርቲስት አለምጸሐይ ወዳጆን ያህል ታላቅ የሰው ሰው የሰጠነ እሱ ነው። አለምዬ ኧረ ተይ ተይ በሌሎች ዘርፍም ያፈራሻቸው አሉ። እባክሽን የተውኔት ልጆሽ ብቻ ሳይሆኑ እኛንም ከፈጠርሻቸው ልጆችሽ ዝርዝር አስገቢን። ሌሎችንም … በክህሎቱ ፈጥሯቸዋል፤ ቀርፆቸዋል … ገንብቷቸዋል። ያው እኔ ለሴቶች አዳላለሁ እንጂ

መሰናበቻ – ለመሰንበቻም – ብቻ ሳይሆን መዝለቂያም የወደድኩትን አገላላጽ ከመግቢያው ለቅምሻ ወስጄ ማሰረጊያውን ለጸሎተ ሥነ – ሕይወት መረጥኩት … እንሆ። ሙሉውን ደግሞ ከሊንኩ አስኪዱት – ክብሮቼ።
“Monday, May 15, 2006
እርሱ Ethiopian_Poet_Laureate_Tsegaye_Gabre-Medhin Honoring the Distinguished Ethiopian Poet Laureate Tsegaye“
መግቢያ በሩ የጸሐፊው „… Mr. CUMMINGS. Mr. Speaker, I rise today to honor the life and work of Ethiopian Poet Laureate Tsegaye Gabre-Medhin who passed away on February 25, 2006 at the age of 69 in his New York home.
Mr. Tsegaye Gabre-Medhin left behind a legacy of poetry and literary works that continue to inspire generations”.
እርገቱ …. የጸሐፊው ደግሞ እንዲህ ይላል …. ለሁልጊዜም የመንፈስ ማህተም።
“Through his literature, Tsegaye’s pride in Ethiopia and love for Africa will live with us forever. by Elijah Eugene Cummings“

ምንጭ …

 የምዕተ ዓመቱ የሥነ ጹሑፍ ምርት 2000 ዓ.ም
http://en.wikipedia.org/wiki/Tsegaye_Gabre-Medhin
Ethiopian Register Vol. no 9, September 1999 „Conversation with Poet Laurete Tsegaye Gebere Medehen“ by Elizabeth W. Giyorgis በጸሐፊ ኤልሳቤጥ ወልደ ጊዮርጊስ ጥልቅና የሰከኑ ትንተናዎች ወስጥ ሃሳቦችና ፎቶዎችን ተውሻለሁ። ለዚህም ነው ከመጽሄት ላይ ፎቶውን ስለወሰድኩት የጥራቱ ጉዳይ እንደፈለኩት ያልወጣልኝ።
http://www.ethiopians.com/tsegaye/ by Professor Negussay Ayele ሥራዎቹን ከሥነ – ተፈጥሮው ጋር ሙሁራዊ ህይወት ያለው ነፍስ ትንተና ….
http://en.wikisource.org/wiki/Honoring_the_Distinguished_Ethiopian_Poet_Laureate_Tsegaye_Gabre-Medhin Honoring the Distinguished Ethiopian Poet Laureate Tsegaye Gabre-Medhin by Elijah Eugene Cummings

ዛሬ ማክሰኞ ነው። ሃሙስ መደበኛ የጸጋዬ ራዲዮ ፕሮግራም አለኝ። ልዩ ዝግጅት ይኖረኛል። እንደ ኤ.አ.አ 27.02.2014 ሰዓት ከ15.00 – 16.00 የቻላችሁ ላይፍ ላይ ማድመጥ ትችላላችሁ። ካልሆነም በማግስቱ አርኬቡ ላይ ማዳመጥ ይችላል። www.lora.ch.tsegaye

ድህረ ገፁንም ጎራ እያላችሁ በቋሚነት በቴክስትና በአውዲዮ የተሰሩባቸውን እነ – ማዕዶትን ስለ ድርጅት ጽንሰ ሃሳብ እንዲሁም ሌሎችን መምሪያዎች ኮምኩሙ። www.tsegaye.ethio.info ለአጠቃላይ መረጃ ደግሞ …
http://ethio.info/tsegaye/Part1LaureateTsegayeWebsiteBigarLfinal.doc በድምጽም በቴክስትም።

በጀግኖቻችን በሐሤት እንኮራለን!
እናት ሀገራችን ኢትዮጵያንና ልጆቿን አምላካችን ይጠብቅልን። አሜን!
እግዚአብሄር ይስጥልኝ።

ኢትዮጵያዉያን በዛሬዉ እለት ረዳት ፓይለት ሐይለመድህን አበራን በመደገፍ ሰላማዊ ሰልፍ አደረጉ

$
0
0

ዋሽንግተን ዲሲ፤ የካቲት 17/2006 (ቢቢኤን )፦ቁጥራቸዉ በመቶዎች የሚቆጠር እትዮጵያዉያንንና ኢትዮጵያዉያን አሜሪካዉያን በዛሬው እለት ዋሽንግተን ዲስ በሚገኘዉ የሲዉዘርላንድ ኤምባሲ ፊትለፊት ሰላማዊ ሰልፍ ያደረጉ ሲሆን የሲዉዘርላንድ መንግስት ረዳት ፓይለቱን ለኢትዮጵያ መንግስት አሳልፎ እንዳይሰጥም ጠይቀዋል።
ጠለፋዉ ለከት ያጣ ጭቆና ዉጤት ነዉ ያሉት ሰላማዊ ሰልፍ አድራጊዎች ሐይለመድህን አንባገነናዉያን የፈጠሩት ስጋት ሰለባ የሆነ ሙያተኛ ቢሆን እንጂ ለማንም ለምንም ስጋት የሚሆን አይደለም ሲሉም ድምጻቸዉን አሰምተዋል።
ረዳት ፓይለት ሐይለመድህን በአንባገነናዊዉ የኢትዮጵያ መንግስት ተንገፍግፎ የዘጠና ሚሊዮን ህዝብ ድምጽን ለማሰማት መስዋእትነት የከፈለ ጽኑ ኢትዮጵያዊ ነዉ፤ ከተስፋሪዎች መጉላላት በስተቀር ማንንም አደጋ ላይ አልጣለም፤ ሐይለመድህን የኛ ጀግና ነዉ! የሲዉዘርላንድ መንግስት እንደወንጀለኛ ሳይመለከተዉ በነጻ ሊለለቀዉ ይገባል ሲሉም ተማጽነዋል።
IMG_6350
የሲዉዘርላንድን መንግስት በመወከል ከኤምባሲ የመጡት ግለሰብም ሰላማዊ ሰልፍ አድራጊዉ ሰላማዊ መሆኑን አድንቀዉ ካመሰገኑ በሗላ የተሰጣቸዉን ደብዳቤ ለውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር እንደሚልኩ በማስታወቅ የተቻለዉን ሁሉ እንደሚያደርጉ ቃል ገብተዋል።

ረዳት ፓይለት ሐይለመድህን አበራን በየካቲት 10/2006 ሁለት መቶ ሁለት ተሳፋሪዎችን የጫነዉን ቦይንግ 767-300 በረራ ቁጥር ET-702 በመጥለፍ ጄኔቫ አሳርፎ የፖለቲካ ጥገኝነት የጠየቀ ሲሆን እስከ አሁን በሲዉዘርላንድ መንግስት ቁጥጥር ስር ይገኛል።
IMG_6353 (1)

የሐይለመድህን ቤተሰቦች ፓይለቱ የአእምሮ ህመም እንዳጋጠመዉ መናገራቸዉ ታዉቋል ።ብዙዎች ግን የኢትዮጵያ መንግስት ያንሰራፋዉ የመብት ረገጣ እንዳይታወቅበት ነዉ ቤተሰቦቹን በማስገደድ የአእምሮ ህመም አለበት እንዲሉ ያደረገዉ በማለት ይተቻሉ።
IMG_6357
ዛሬ በዋሽንግተን ዲሲ ሰላማዊ ሰልፍ ያደረጉ እትዮጵያዉያንንና ኢትዮጵያዉያን አሜሪካዉያን ረዳት ፓይለቱ ጤነኛ ነዉ የአእምሮ ህመም የሚለዉ አሉባልታ በኢትዮጵያ መንግስት የተፈበረከ ነዉ ሲሉ ያጣጥላሉ።

Photo credit: Kebadu belachew

ኢትዮጵያዉያን በዛሬዉ እለት ረዳት ፓይለት ሐይለመድህን አበራን በመደገፍ ሰላማዊ ሰልፍ አደረጉ (VIDEO)

‘‘ፋሽዝም’’ በኢትዮጵያ!

$
0
0

በቅዱስ ዬሃንስ

ኢትዮጵያ በወያኔ ፈላጭ ቆራጭ ቡድናዊ አገዛዝ ስር ከወደቀችበት እነሆ ሁለት አስርተ ዓመታት ነጐዱ። ወያኔ ስልጣን ላይ ሲወጣ ካለፈው የተሻለ የዲሞክራሲ ለውጥ ይመጣል የሚል በብዙ ሰዎች ዘንድ የተስፋ ጭላንጭል ተጥሎለት ቢኖርም “ጅብ እስኪነክስ ያነክስ” እንዲሉ ስልጣናቸውን ካደላደሉ በኋላ ግን ተስፋ የተጣለለትን ዲሞክራሲ ደብዛውን በማጥፋት “ከፋፍለህ፣ በሆዱ ይዘህ፣ አሸብረህ፣ አደናግረህ፣ አናቁረህና አደንዝዘህ ግዛ” የሚለውን ሌሎች አምባገነን መንግስታት የሚከተሉትን የጡንቻ አገዛዝ ዘይቤ የዲሞክራሲ ሽፋን በመስጠት ዘላለማዊ ስልጣናቸውን ለማጠናክር ሲሉ በበለጠ ሲጠቀሙበት መቆየታቸው የአደባባይ ሚስጢር ሆኖ ቆይቷል።

በአገራችን ኢትዮጵያ በሥልጣን ላይ ያለው የወያኔ አገዛዝ በዓለም ዙሪያ በተለያየ ዘመን ወደ ሥልጣን ከመጡት መሰል ፀረ-ሕዝብ መንግሥታት ቢብስ እንጂ በምንም መልኩ የተሻለ አይደለም። ፋሽዝምን እንቃወማለን፣ እናወግዛለን እያለ በጫካ ያናፋ የነበረው ወያኔ ዛሬ በዲሞክራሲ ድባብ ሥር እየተገበረው ያለ አገርና ሕዝብን ማዋረድና መዝረፍ፣ መቀጣጫ እያለ በግፍ ማሰርና መግደል ምን ተብሎ ሊጠራ ነው? በአዲስ አበባ ፣ በጋምቤላ ፣ በአዋሳ ፣ በወለጋ ፣ በሰሜን እና በአራቱም ማእዘን የኢትዮጵያ ክልሎች በየእለቱ በወያኔ ታጣቂዎች እየተካሄደ ያለውን የጅምላ ጭፍጨፋ ምን ብለው ይጠሩታል?

ወያኔ ኢትዮጵያን ሲቆጣጠር ተሸክሞት የመጣውን በቀል አማራው፣ ኦሮሞው፣ ጋምቤላው፣ አፋሩ፣ ኦጋዴኑ ወዘተ. ዘር የማጥፋት ተግባሩን ፈጽሞታል፤ አሁንም እያጠፋ፣ እየገደለ በየወህኒ ቤቶቹ እየማገደው ነው። ይዞት የመጣው ድህነትና በሽታን ብቻ ነው። ፖሊሲው የኢትዮጵያን ሕዝብ ከዓለም ሃገሮች በድህነት ከወለል በታች ያደረገ ስርዓት ነው። የኢትዮጵያ ገበሬ የመሬቱ ባለቤት በነበረበት ወቅት እራሱን እና ቤተሰቡን አብልቶ ቀሪውን ለገበያ በማቅረብ ሕዝቧ እንደ አቅሙ በልቶና ጠጥቶ ያድር ነበር። የወያኔ መንግስት መሬት የመንግሥት ነው ብሎ በማወጁ የኢትዮጵያ ሕዝብ በገጠሩም በከተማም መሬት አልባ ሆኗል። የኢትዮጵያ ሕዝብ በገዛ ሃገሩ ሁለተኛ ዜጋ ከመሆኑ የተነሳ ሲሞት እንኳን የሚቀበርበት ቦታ ያጣ ሕዝብ ሆኗል። የዚህ ጽሁፌ ዋና አላማ የወያኔ መንግስት የፋሽስት አገዛዝ ስለመሆኑ ምሳሌዎችን አንድ ሁለት በማለት ነቅሸ በማሳየት ማስረገጥ ሲሆን ወያኔ ከምስረታው ጀምሮ ያካሂድ የነበረውን የንፁሃን ወገኖቻችንን ጭፍጨፋ ለማስረጃነት በማንሳት ለማሳየት እሞክራሉ።

• ወያኔ በ1969 መጀመሪያ በትግራይ ሰላማዊ ዜጋ ላይ ግድያ በመፈፀም ፋሽስታዊ ጉዞውን ሀ ብሎ ጀመረ። ግድያው ሳያንሰው የንፁሃን ዜጐችን ሃብትና ንብረትም ወረሰ። ከደደቢት በረሃ የጀመረውን አማራ የትግራይ ሕዝብ ጠላት ነው በማለት በተለያዩ ጊዜያትና ቦታዎች አማራውን በመጨፍጨፍ የዘር ማጥፋት ወንጀልም ፈጽመዋል። ለሴቶች በግዳጅ የማምከኛ መድሃኒት በመስጠት የአማራው ቁጥር እንዳይጨመር አድርገዋል። ከኖረበት ቀየውና መሬቱ በግዳጅ እንዲፈናቀል አድርገዋል።
• ወያኔ ኢትዮጵያን እንደተቆጣጠረ በ1984/5 መጀመሪያ ጀምሮ በኦሮሞ ሕዝብ ላይ መጠነ ሰፊ የጥቃት ዘመቻ በመክፈት የግድያ፣ የቤት ማቃጠል፣ ንብረቱን መዝረፍና ከፍ ያለ ሰቆቃ አደረሰ። እንደ አማራው ሁሉ ከመኖሪያ ቦታውና ከመሬቱ ላይ ተፈናቅሏል። የኦነግ አባል ናችሁ እየተባሉ በሺዎች የሚቆጠሩ ያለምንም የፍርድ ውሳኔ ወደ ወህኒ ወርደዋል። በየቦታው በከፍተኛ ትምህርት ተቋሟት የሚማሩት የኦሮም ልጆች ከትምህርታቸው ተባረዋል። የተባረሩትም፣ መባረራቸው አልበቃ ብሎ ለእስር ተዳርገዋል፤ የተገደሉትንም ቤት ይቁጠራቸው። ደጉና ሩህሩሁ የኦሮሞ ሕዝብ ከእርሻው ተፈናቅሎ የረሃብና የበሽታ ሰለባ በመሆን የፋሽስቱ ወያኔ የግፍ ፅዋ ገፈት ቀማሽ ከመሆን አላለፈም።
• ወያኔ በጋምቤላ አኝዋኮች ላይ የፈጸመው የዘር ማጥፋት ወንጀልን ማንም ይረሳልዋል ብየ አላስብም? ሕዝቡ ከመሬቱ ተፈናቅሎ አብዛኛው በጎረቤት ሃገሮች ስደተኛ ሆነው በየሃገሩ እየተንከራተተ በችግር ላይም ይገኛሉ።
• የኦጋዴን ሕዝብም የዘር ማጥፋት ወንጀል ተፈጽሞበታል። ቤት ንብረቱ በወያኔ ወታደሮች ተቃጥሎበታል፤ ሴት ልጆቹና ሚስቶቹ ተደፍረውበታል። በተጨማሪም ከመሬቱ ላይ ተፈናቅሎ ለስደት ተዳርጓል።
• የአፋር ሕዝብም በሌሎቹ የኢትዮጵያ ጎሳዎች የደረሰው ደርሶበታል፣ እየደረሰበትም ይገኛል። የኢትዮጵያን ሕዝብ ከማሰቃየት ባለፈ ደግሞ የኢትዮጵያን ዳር ድንበር ለሱዳን መንግሥት ሸጠዋል። ሃገሪቱን ካለባህር በር አስቀርተዋል። የሃገር ሃብትና ታሪካዊ ቅርሶችን አውደመዋል፣ ሸጠዋል።
እንደው በደፈናው በአገራችን ታሪክ ውስጥ በሕዝባችን ከቶም እንደ አሁኑ ሳንጃ በአንገቱ ላይ ተወድሮ ጦር ተሰብቆበት የሚገኝበት የፋሽስታዊ አገዛዝ ጊዜ የለም። ፋሽዝም ዛሬ በወያኔ/ህወሃት ጊዜ ነግሷል ሥርም ሰዷል። በሥልጣን ላይ ለመቆት፣ ሃብቷን በዝብዞና ሽጦ ለማፈራረስ በታቀደው የአገዛዝ ሽብር ተግባር፣ ፋሽዝም በዴሞክራሲ ታዛ ሥር ወያኔ በኢትዮጵያና ኢትዮጵያዊነት ላይ እየፈጸመው ያለ ለመሆኑ ሁሉም አገር ወዳድ ዜጋ ይረዳውል ብየ አምናለሁ። ፋሽስት ሕዝብ ይጨፈጭፋል፣ ያስፈራራል፤ ፋሽስት የማደናገሪያ ፕሮፓጋንዳን ያስፋፋል፣ ውሽት ይዋሻል፤ ፋሽስት ትምክህተኛና ጦርነት ፈላጊ ነው። ፋሽስት ራስ ወዳዶችን፣ ሆዳሞችን፣ ግብዞችን፣ ዱርየዎችን መሳሪያ ያደርጋል፤ ፋሽስት ድርጅቶችን ያስፋፋል፣ ተለጣፊ ያበዛል ወዘተ። እንግዲህ የፋሽስት አገዛዝ ባህርያትን ማንሳቴ ወያኔን በነዚህ ባህሪያትም መዝነን ፍረጃችንን ለማጠናከር ይረዳን ዘንድ በማሰብ ነውና መዝኖ ፍርድ መስጠቱን ለእናንተው ትቻለሁ።

ወደ ሥልጣን ከመጣበት ጊዜ ጀምሮ እጁን በንፁኃን ዜጎች ደም የታጠበው የወያኔ አገዛዝ ሕጋዊ የአምልኮት ነፃነታቸው ያለምንም የአገዛዙ ጣልቃገብነት እንዲከበር የጠየቁ የእስልምና ሃይማኖት ተከታይ ኢትዮጵያውያንን በጅምላ በሃይማኖት አክራሪነትና አሸባሪነት ወንጅሎ የግድያ ወንጀል ፈጽሟል። በክርስቲያን እምነት ተከታይ ወገኖቻችንም ተመሳሳይ ግፍ ሲፈፀምባቸው ተመልክተናል። ገዳማትን ማፍረስና መነኮሳትን ማሳደድና መግደል የወያኔ መለዮው ሆኗል። ወያኔ ንፁኃን ዜጎችን ከማሰቃየት፣ ከማሰርና ከመግደል የታቀበበት ወቅት ከቶውንም የለም፤ አልታየምም። ድብደባው፣ ማሰሩና ግድያው እየተፈጸመ ያለው በሁሉም የሃገሪቷ ክፍሎች በሚኖሩ ንፁሃን ዜጐች ሲሆን በግፍና በገፍ ወደ እሥር ቤት የማጎር እርምጃዎች ያልርኅራሄ ተፈጽመዋል፤ እየተፈጸሙም ነው።

ውድ የኢትዮጵያ ሕዝብ ሆይ በኢትዮጵያዊ ትዕግሥትና አርቆ አስተዋይነት በፋሽስቱ ወያኔ ወገን ሲደበደብ፣ ሲባረር፣ ሲገደል፣ ሃብት ንብረቱ ሲዘረፍ፣ ዳር ድንበሩ ሲወሰድ፣ በቋንቋ ልዩነት ሲመደብ፣ የተማረ ወገን ሲገደልና ሲሰደድ፣ አገር ለውጭ ባለሃብት ስትሽጥ፣ ይህ ሁሉ ሲሆን እስከ አሁን በደልን ተሸክመህ በዝምታ ታግሰሃል። ዛሬ በፋሽስቱ ወያኔ ኢትዮጵያ ተደፍራለች፣ ሕዝቧ ተዋርዷል፣ የታሪክ ክብሯ ተንቋል። ለብዙ ሺህ አመታት የኛ ቀደምት ትውልዶች አጥንትና ደማቸውን በማፍስስ ታፍራና ተፈርታ የኖረች አገር ዛሬ በዚህ ወቅት የትውልድ መካን ሆና ጥቃቱና ጥፋቱ እጅግ ተነባብሯል። ኢትዮጵያዊ ወገኔ ሆይ! ፍርሃት ከአደጋ የመከላከያ ባህሪ እንጂ እየሸሹ ለመጥፋትና ለመሞት አይደለም። ይህ ጭቆናና ጥቃት ሊያበሳጭ፣ ሊያናድድህና ሊያስቆጣህ ይገባል። ሰው ነህና ለመብትና ለነፃነት መታግልና ለመጭውም ትውልድ ለልጆችህ አገር ማቆየት ይኖርብሃል። የኛ ቀደምት አባቶችና እናቶች እኛ ሞተን አገር ትኑር ብለው ለኢትዮጵያ ታላቅ መስዋዕትነት ከፍለዋል። ታሪክ ምስክርነትዋን መዝግባለች። ዛሬም የኢትዮጵያዊያን ወኔና ጀብዱ፣ አትንኩኝ ባይነት ይደገም። ወያኔ ኢትዮጵያዊነት የሌለው አረመኔ ፋሽስት ነውና፤ መወገድ አለበት። ስለዚህ ለትዕግሥት ገደብ እንስጥ፣ አንዋረድ ፣ ትውልድ እንጠብቅ፣ አገርና ሕዝብ እናድን።

ድል ለጭቁኑ የኢትዮጵያ ህዝብ!

ለአስተያየትዎ፡ kiduszethiopia@gmail.com አድራሻየ ነው።

ድሬዎች ለሰማያዊ ፓርቲ፡ “ኢሕአዴግ ክፉ መንግስት ነው፤ አብረናችሁ እንታገላለን”

$
0
0

*‹‹ወደ ድሬዳዋ መጥታችሁ ስላነጋገራችሁን ደስ ብሎናል›› የድሬዳዋ ከተማ ነዋሪዎች፤

ዘገባ በጌታቸው ሽፈራው

ድሬዳዋ፡- ሰማያዊ ፓርቲ (ሰማያዊ) በወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳዮችና በፓርቲው የትግል አቅጣጫ ዙሪያ ከድሬዳዋ ከተማ ነዋሪዎች ጋር የካቲት 16 ቀን 2006 ዓ.ም በከተማዋ ተገኝቶ ባደረገው ህዝባዊ ስብሰባ ላይ ተወያየ፡፡

በስብሰባው ላይ ፓርቲው እስካሁን ያደረጋቸውን ህዝባዊ ትግሎችና ያስገኛቸውን ዋና ዋና ውጤቶች በድርጅት ጉዳይ ኃላፊው አቶ ጌታነህ ባልቻ በኩል ለነዋሪዎች ገለጻ አድርጓል፡፡ በተጨማሪም በፓርቲው ሀገራዊ አላማና የፖለቲካ ፕሮግራም ዙሪያ ለከተማዋ ነዋሪዎቹ ገለጻ ተደርጎላቸዋል፡፡
Birhanu Tekeleyared, engreer yilikal and Engeener Getaneh Balcha
‹‹ወደ ድሬዳዋ ከተማ መጥታችሁ ስላነጋገራችሁን ደስ ብሎናል›› ያሉት የከተማዋ ነዋሪዎች፣ ‹‹ምርጫ ሲደርስ ብቻ ወደ እኛ የመምጣቱን የቆየ ልምድ ሰብራችሁ ከአሁኑ ራሳችሁን ስላስተዋወቃችሁንና የትግል አጋራችሁ እንድንሆን ስለፈቀዳችሁ እናመሰግናለን›› ብለዋል፡፡ በስብሰባው ላይ የተገኙ አንድ አስተያየት ሰጭ በድሬዳዋ ከተማ ስላለው ወቅታዊና የፖለቲካ ሁኔታ አንስተው፣ በኢህአዴግ አገዛዝ የድሬዳዋ ነዋሪዎች እየደረሰባቸው ያለውን በደል አጋልጠዋል፡፡

‹‹ኢህአዴግ የማይገባበት ነገር የለም፤ ወዳጅ መስሎ በመሐላችን እየገባ ያጣላናል፡፡ ኢህአዴግ ክፉ መንግስት ነው፡፡ እንኳን መጣችሁልን እንጂ አብረናችሁ እንታገላለን፤ ለነጻነታችን ለመታገል ሞትን አንፈራም›› ሲሉ ተደምጠዋል፡፡

በድሬዳዋው ህዝባዊ ስብሰባ ላይ ከህዝቡ በርካታ ጥያቄና አስተያየቶች የተሰነዘሩ ሲሆን በፓርቲው ከፍተኛ አመራሮችም ምላሽ ተሰጥቷቸዋል፡፡ የድሬዳዋ ነዋሪዎች መሬትን፣ ብሄር ብሄረሰብን፣ ሰንደቅ አላማን፣ የታሰሩ ጋዜጠኞችንና ፖለቲከኞችን፣ ምርጫ-2007ን፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች የውህደት አጀንዳን እና ሌሎች በርካታ አንኳር ጉዳዮችን አንስተዋል፡፡

የፓርቲው ሊቀመንበር ኢ/ር ይልቃል ጌትነት ለተነሱት ጥያቄዎች ምላሽና ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡ በተለይ የብሄር ብሄረሰቦችን መብት በተመለከተ ‹‹በኢትዮጵያ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች እንዳሉ እንገነዘባለን፡፡ ነገር ግን ፓርቲያችን በግለሰብ ነጻነትና መብት ያምናል፡፡ ምክንያቱም የግለሰብ መብት ከተከበረ የቡድን መብትም አብሮ እንደሚከበር እናውቃለን፡፡ እስኪ ለአብነት የግለሰብ መብት ተከብሮ የቡድን መብት የማይከበርበት ሁኔታ ካለ እናንሳ…የለም፡፡ ስለዚህ ትኩረታችን በግለሰብ መብት መከበር ከሆነ የቡድን የሚባሉ መብቶችም አብረው መከበራቸው እሙን ነው›› በማለት አስረድተዋል፡፡

ሰማያዊ ፓርቲ ‹ሞደሬት ሊብራሊዝም› አይዶሎጅን እንደሚያራምድ የተናገሩት ሊቀመንበሩ፣ የመሬትና ሌሎች ተያያዥ ጉዳዮች ከዚህ መነሻነት የተቃኙ እንደሚሆኑ ጠቅሰዋል፡፡ ኢ/ር ይልቃል ከሌሎች ፓርቲዎች ጋር ያላቸውን ግንኙነት በተመለከተም ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡ ‹‹ሰማያዊ አብሮ በመስራትና በትብብር ያምናል፡፡ ነገር ግን ሁሌም ምርጫ ሲደርስ እንደሚደረገው በሩጫ ወደ ውህደት ለመግባት አንፈልግም፡፡ ካለፉት የሌሎች ተሞክሮዎች ብዙ ተምረናል፡፡›› ብለዋል፡፡

semayawi party Drie Dawa
ሰማያዊ ፓርቲ ድሬዳዋ በነበረው ቆይታ በዚያው የከፈተውን ቢሮና የአካባቢውን መዋቅር የማስተዋወቅና የማጠናከር ስራም ሰርቷል፡፡ ፓርቲው በሌሎች ከተሞችም ተመሳሳይ ስራ መስራቱን አጠናክሮ እንደሚቀጥል ለማወቅ ተችሏል፡፡

Over 1 million babies die on day of birth yearly

$
0
0

Save the Children argues that most of these deaths are preventable

London: More than a million babies around the world die on the day of their birth yearly and a million more are stillborn, according to Save the Children, which argues that most of these deaths are preventable.

Save the Children says many baby deaths could be prevented by something as simple as hand-washing or sharing a mother’s body heat.

Save the Children says many baby deaths could be prevented by something as simple as hand-washing or sharing a mother’s body heat.


Although great strides have been made in reducing the numbers of children dying under the age of five in the past decade numbers have halved from 12 million to 6.6 million, there has not been enough progress in reducing the preventable deaths of newborn babies, says the charity.

Most of the deaths occur in developing countries. Some lives could be saved by simple interventions such as handwashing to prevent infections and “kangaroo care”, where mothers “incubate” their premature babies by keeping them warm through skin to skin contact.

The charity says there needs to be an increase in the number of women delivering with the help of a trained midwife or health worker, as 1.2 million deaths occur during labour. In cases of obstructed labour, mother and baby are likely to die without a caesarean section.

Save points to the global shortage of health workers who have the skills to help. It is estimated that 7.2 million more midwives, nurses and doctors are needed.
Every year, 46 million women give birth without the assistance of a professionally qualified person, says its report, Ending Newborn Deaths. In sub-Saharan Africa, half of all births are not attended by a midwife or other properly qualified health worker; in Ethiopia, that drops to just 10 per cent. But there are stark inequalities within countries; — in the richest fifth of households in Ethiopia, there are health professionals at 46 per cent of births, compared with two per cent among the least well-off. Justin Forsyth, the chief executive of Save the Children, said: “The first day of a child’s life is the most dangerous and too many mothers give birth alone on the floor of their home or in the bush without any life-saving help. We hear horror stories of mothers walking for hours during labour to find trained help, all too often ending in tragedy.

“It’s criminal that many of these deaths could be averted simply if there was someone on hand to make sure the birth took place safely and who knew what to do in a crisis.”
In countries such as the Democratic Republic of the Congo and the Central African Republic, women have to pay for emergency care — usually a caesarean — and there have been reports of some women being detained at the hospital until their families find the money.

Save the Children says the Millennium Development Goal to reduce child deaths by two-thirds by 2015 will not be met unless childbirth is made safer. By 2025, the charity says, every birth should be attended by a trained and equipped health worker and user fees for all maternal, newborn and child health services should be removed.


Health: ባለቤቴሽን ከሌላ ሴት ጋር አልጋ ላይ ብታገኚው ወዲያው ፍቺን ከማሰብሽ በፊት ይህን አንብቢ

$
0
0

ባለቤቴን ከሌላ ሴት ጋር አልጋ ላይ የያዝኩት ዕለትን የመሰለ መጥፎ ቀን በህይወቴ አጋጥሞኝ አያውቅም፡፡ እንደዚህ አይነት ነገር ያደርጋል ብዬ አስቤ አላውቅም፡፡ በጉዳዩ ዙሪያ ከባለቤቴ ጋር ስንነጋገር ‹‹ውዴ እወድሻለሁ፤ ነገር ግን ልጅቷንም እወዳታለሁ›› አለኝ፡፡ ይህን ሲለኝ እምባዬን መቆጣጠር አቃተኝ፡፡ እየቆየሁ ስሄድ ለባለቤቴ ወደ ሌላ ሴት መሄድ ጥፋቱ የእኔ እንደሆነ ማሰብ ጀመርኩ፡፡ ባለቤቴን በትክክል ላስደስተው ብችል ኖሮ እንዲህ አይነት ውሳኔ ላይ ላይደርስ ይችል ይሆን?
ሳራ

love and Divorce
የኢሳያስ ከበደ ምላሽ፦ ብዙ ሚስቶች ባሎቻቸው ወደ ሌላ ሴት በሄዱ ቁጥር ጥፋተኛ የሚያደርጉት ራሳቸውን ነው፡፡ ‹‹እኔ በአልጋ ላይ ጨዋታ ባለቤቴን ባስደሰተው ኖሮ ከሌላ ሴት ጋር አይተኛም ነበር›› ብለው ያምናሉ፡፡ ይህ አስተሳሰብ የሚስቶች ብቻ ሳይሆን የባሎችም ነው፡፡ ባሎችም ሚስታቸው ከሌላ ወንድ ጋር መዳራቷን ሲያውቁ ‹‹ሚስቴን ላስደስታት አልቻልኩም ማለት ነው›› ብለው ነው የሚያስቡት፣ እውነቱ ግን ይሄ አይደለም፡፡

ከትዳር ውጪ ዝሙት ሲፈፅም ባል ወይም ሚስት ራሳቸውን ጥፋተኛ አድርገው ማሰባቸው ተገቢ አይደለም፡፡ ጥፋቱ ዝሙትን የፈፀመው ሰው እንጂ የሌላው ወገን አይደለም፡፡ ባልና ሚስት በመካከላቸው የዚህ አይነት ችግር ሲከሰት በፍጥነት ለመለያየት ከመወሰንና ከማኩረፍ ይልቅ በረጋ መንፈስ ለመነጋገር መሞከሩ ተገቢ ነው፡፡ ሳራ ባለቤቷን በግልፅነት ልታነጋግረው ሞክራለች፡፡ ባለቤቷም ስለ ሁኔታው ያለውን አቋም ሲያሳውቃት ትቆጣለች ወይም ትናደዳለች ብሎ ሳይሆን ስሜቱን ነው፡፡ ባለቤቷ ሁለተኛ የዚህ አይነት ድርጊት አልፈፅምም ብሎ በድብቅ ማድረጉን ቢቀጥልስ? ከፍተኛው የህሊና ጉዳት በሳራ ላይ የሚደርሰው የዚያን ጊዜ ነው፡፡

ሳራ በሰከነ መንፈስ ባለቤቷን በድጋሚ እንዲህ ብላ ልታናግረው ይገባል፡፡ ‹‹በትዳር ሕይወታችን ላንተ ያለኝ ፍቅር አሁንም አለ፡፡ በጋብቻችን ዕለት የገባህልኝን ቃል አሁንም አስታውሰዋለሁ፡፡ ነገር ግን አሁን እኔን ብቻ ሳይሆን ልጅቷንም እንደምትወዳት ገልፀህልኛል፡፡ እኔ ሚስትህ ነኝ፡፡ እኔንና እሷን በእኩል ደረጃ ልትወደን የቻልክበት ምክንያት አልገባኝም፡፡ በጋብቻችን ዕለት በተባባልነው ቃል መሰረት ቃላችንን ልንጠብቅ ይገባል፡፡ ይህ ካልሆነ ደግሞ በሰላም ልንለያይ ይገባል››
‹‹በትዳር ህይወታችን ላንተ ጥሩ ሚስት ለመሆን የዘወትር ምኞቴ ነው፡፡ ካንተ ሌላ ገላዬን ለማንም አሳልፌ ገልጬ አላውቅም፡፡ አንተ ግን ከሌላ ሴት ጋር ተኝተሃል፡፡ በዚህ ሁኔታ ግን ለመቀጠል ይቸግረኛል፡፡ ከእሷ ጋር መቀጠል ከፈለግህ ልትፈታኝ ትችላለህ፡፡ በግድ ባል ሆነህ እንድትቆይ ማስገደድ አልችልም፡፡ ይሄ ትዳር ሊሆን አይችልም››

የሳራ ባለቤት ይህንን ካዳመጠ በኋላ በፍፁም ደስተኛ ሊሆን አይችልም፡፡ በሚስቱ ላይ የፈፀመው በደል ቁልጭ ብሎ ነው የሚታየው፡፡ የሚስቱ ንግግር ለባሏ ያላትን ፍቅርና አለኝታነት የሚያሳይ በመሆኑ እግሯ ላይ ወድቆ ይቅርታ ለመጠየቅ አያመነታም፡፡ ከሚስቱ ሌላ የለመዳት ሴት ሚስቱ ልትሆን እንደማትችል የሚረዳው ወዲያውኑ ነው፡፡ የሚስቱ ይቅር ባይነትና ትህትና ባለቤቷን በእጇ ለማስገባትና ለመመለስ ትልቅ አስተዋፅኦ ነው ያለው፡፡

ሳራና ባለቤቷ አሁን በጥሩ የትዳር ህይወት ውስጥ ነው ያሉት፡፡ የሳራ ትዕግስትና ርህራሄ ባለቤቷ ራሱን እንዲመረምርና ይቅርታ እንዲጠይቃት አስችሏል፡፡ ሳራ ባለቤቷን አልጋ ላይ እንደያዘችው ለፖሊስ ደውላስ ቢሆን? ዛሬ ፍቅር የሞላበት ትዳር ይፈርስ ነበር፡፡S

የኢትዮጵያ ሴቶች ጉዳይ ሚ/ር ዘነቡ ታደሰ ዩጋንዳ የጸረ ጌይ ሕግ ማውጣቷን ተቹ

$
0
0

(ዘ-ሐበሻ) ኢትዮጵያ የሴቶች ጉዳይ ሚኒስትር የሆኑት ዘነቡ ታደሰ ኡጋንዳ የጸረ ጌይ አዋጅ ማውጣቷን መተቸታቸውን ሃፊንግተን ፖስት የተባለው ጋዜጣ ሚኒስትሯ በትዉተር ገጻቸው የጻፉትን አስተያየት አያይዞ ባቀረበው ዘገባው አስታወቀ። እናት ድርጅታቸው ኢሕአዴግ ከዚህ ቀደም በኢትዮጵያ የአፍሪካ ጊዮች ስብስባ እንዲደረግ መፍቀዱና በጁፒተር ሆቴል ይደረጋል በተባለው በዚህ ስብሰባ ከፍተኛ ተቃውሞ መነሳቱ ይታወሳል።

በትዊተር ገጻቸው ዘነቡ ታደሰ ኡጋንዳ የጸረ ጌይ (ጸረ የተመሳሳይ ጾታ ግንኙነትን) አዋጅን ካጽደገቀች በኋላ በእንግሊዘኛው There is no place for hate, discrimination in my beloved Africa. It’s not Governments’ business to make dress code or anti-gay laws #Uganda.” ብለው ጽፈዋል ያለው ሃፊንግተን ፖስት የኡጋንዳን መንግስት ሕጉን በማጽደቁ ተችተዋል ብሏል።

“ስለአለባበስም ሆነ የጸረ ጌይ ሕግ ማውጣት የመንግስት ጉዳይ መሆን የለበትም” በሚል የተናገሩት የኢትዮጵያ የሴቶች ጉዳይ ሚኒስተር ዘነቡ ታደሰ የጌይን ሕግ መጽደቅ ይደግፋሉ በሚል መነጋጋሪያ ሆነዋል።

ዘነቡ ታደሰ በትዊተር ገጻቸው የጻፉት የሚከተለው ነው፦

zenebu Tadesse

በአባይ ግድብ ጉዳይ ኢትዮጵያ ከሱዳን ጋር እየተነጋገርኩ ነው አለች

$
0
0

ዋሽንግተን ዲሲ፤ የካቲት 18/2006 (ቢቢኤን) ፦አራት ነጥብ ሰባት ቢሊዮን ዶላር ይፈጃል የተባለዉ ግድብን እንገነባለን በማለት የኢትዮጵያ መንግስት በቦንድ ስም ገንዘብ ለመሰብሰብ ያደረገዉ ሙከራ እምብዛም አለመሳካቱ ይታወቃል። የኢትዮጵያ መንግስት የግንባታዉ ፕሮጀክት ሰላሳ አራት ከመቶ ተጠናቋል ቢልም ግብጽ ባሰማችዉ ተቃዉሞ የግድቡ ግንባታ መስተጓጎሉን የመገናኛ ብዙሗን ዘግበዋል።
ABAY
የኢትዮጵያ ዉሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የሆኑት አቶ አለማየሁ ተገኑ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ “ኢትዮጵያ ችግሩን ለመቅረፍ ከሱዳን ጋር ዉይይት ጀምራለች” ሲሉ ገለጸዋል። ግብጽን ወደ ዉይይቱ ሒደት ለማምጣት እየተጣረ መሆኑን የገለጹት ሚኒስቴር ሒደቱ ምን እንደሚመስል ግን ያመላከቱት ነገር የለም።

ሱዳንና ግብጽ ከግድቡ ተጠቃሚ እንደሚሆኑ ኢትዮጵያ ብትገልጽም፤ ሁለቱ አገራት ግን ለጉዳዩ አዎንታዊ ምላሽ ሲሰጡ አልተስተዋልም። ግብጽ ሰማኒያ ከመቶ የሚሆነዉ የዉሃ ሐብቷ ከአባይ እንደሚመጣ ይታወቃል፤ የአባይን ጉዳይ እንደ ህልዉና ስለምትመለከትዉ የህዝብ ድጋፍ የሌለዉ የመላኒየሙ ግድብ እንደምን ዉጤታማ ይሆናል የሚለዉ ጉዳይም አጠያያቂ እየሆነ ነዉ።

ግድቡን ለመገንባት እስከ ሐያ ሺ የሚደርሱ ኢትዮጵያዉያን መፈናቀላቸው የታወቀ ሲሆን 70 ሚሊዮን ኩቢክ ሜትር ዉሃን ያከማቻል ተብሎ የተነገረት ግድብ ከፈነዳ ከፍተኛ የዉሃ መጥለቅለቅ ሊፈጥር ይችላል የሚል ስጋት አለ።

ኢትዮጵያ ግድቡ በአዉሮፒያኑ ቀመር 2017 ሲጠናቀቅ እስከ ስድስት ሺ ሜጋ ዋት የሚደርስ የኤለክትሪክ ሐይልን ለማመንጨት ብቃት ይኖረዋል ትላለች። ይህ ዉጥን ከግድቡ ባላንጣዎች ከሱዳናን ግብጽ ብቻ ሳይሆን” አባይ ከመገደቡ በፊት የመብት ጥሰቱ ይከበር” ከሚሉ ኢትዮጵያዉያንም ጭምር ጽኑ ተቃዉሞ እየገጠመዉ ነዉ። ኢትዮጵያ ከፕሮጀክቱ ዋነኛ ባላንጣ ከግብጽ ጋር በቀጥታ መነጋገር ሲገባት፤ ከሱዳን ጋር ዉይይት መጀመሯ ለምን እንደሆነ የዉሃና ኢነርጂ ሚኒስቴሩ ግልጽ አላደረጉም።
ABAY 2
በተያያዘ ዜናም ጠቅላይ ሚኒስቴር ሐይለማሪያም ደሳለኝ ቀደም ሲል በህዳር 24/2006 ወደ ሱዳን ተጉዘዉ የስራ ጉብኝት ማድረጋቸዉንና ህወሃት የተመሰረተበትን 39ኛ አመት ለማክበር የሱዳኑ ፕሬዝዳንት ኡመር ሐስን አልበሽር በየካቲት 11/2006 ወደ መቐሌ መጓዛቸዉን ይታወቃል።ይህ ከወትሮ የተለየ ቁርኝት እንደምን ተከሰተ በማለት ጥያቄ የሚያነሱ ወገኖችም አሉ።

የሱዳን የዉጪ ጉዳይ ሚኒስቴር አሊ አልቀርዲ በህዳር 23/2006 ኢትዮጵያና ሱዳን ያላቸዉን የድንበር ልዩነት አስወግደዉ መስማማታቸዉን ይፋ አድርገዋል።

ኢትዮጵያ ድንበሯን ለሱዳን ቆርሳ ለመስጠት መስማማቷ ከጉዳዩ ጋር ግንኙነት ያለዉ ብቻ ሳይሆን ህወሃት በስልጣን ለመቆየት የተቃዋሚ ሐይላትን ለመግታት አጎራብች አገራትን እየደለለ ነዉ የሚሉም አሉ።ህወሃት ስልጣኑ በህዝብ ከተወሰደ ሐብትን ወደ አጎራባች አገሮች አሽሽቶ ለመደላደል የሚያደርገዉ ሴራ ይኖራል በማለት ጉዳዩን ከመልካዓምድራዊ የፖለቲካ አለመረጋጋት ጋር የሚያይዙም አሉ።

አንድንድ ተንታኞች ደግሞ አባይን መገደብ የሚለዉ ሐሳብ ሶስት ዲሞክራሲያዊ ያልሆኑ አገራት አንባገነናዊ መንግስቶች በስልጣን ላይ ለመቆየት የሚያደርጉት ወከባ ነዉ፤ የኢትዮጵያ መንግስት በግድቡ ስም ገንዘብ ሲሰበስብ፤ ሱዳንና ግብጽ ደግሞ ብሔራዊ የሆነ ስጋት እንዳንዣበበ በመስበክ ህዝብን የሚያደናግሩበት ትርኢት ነዉ ይላሉ።

ቀድም ሲል ባሶንዳ በሚባለዉ የሱዳን የጠረፍ ከተማና አካባቢ 77 ኢትዮጵያዉያን በሱዳናዉያን መገደላቸዉን ቢቢኤን ዘግቦ ነበር ።ይህ ከጉዳዩ ጋር ግንኙነት እንዳለዉ ባይታወቅም፤ የሚታወቀዉ ነገር ግን የኢትዮጵያ ዉሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የሆኑት አቶ አለማየሁ ተገኑ የአባይ ግድብ አስመልክቶ ከሱዳን ጋር ዉይይት መኖሩን መናገራቸዉ ነዉ።

በሱዳን ስለሞቱት 77 ኢትዮጵያዉያን የሚናገር ይኖር ይሆን?የኢትዮጵያ እና የሱዳን መንግስታት ስል ድንበር ስምምነት፣የጋራ ስለሆነ ደህነነትና ጥበቃ፣ህገወጥ የሆነ የሰዎች ዝውዉርን ስለመግታት፣የኤለክትሪክ ሐይልን ስለመጋራት፣የአባይን ግድብን አስመልክቶ ስለሚደረጉ ዉይይቶች ብቻ ነዉ እየገለጹ ያሉት።

የወያኔ ትግሬዎች በጉንደት፤በጉራዕ፤በዶጋሊ፤….ጦርነቶች የሚዋሹት ውሸት ሲመረመር

$
0
0

Dogali war and Tigray Ethiopia
ጌታቸው ረዳ (ኢትዮጵያን ሰማይ ድረገጽ አዘጋጅ)

መጀመርያ በዚህ የአመቱ ምርጥ ብየ በምጠቅሰው ጥቅስ ልጀምር፦”የመሬት ላራሹ” ጩኸት ውጤቱ “መሬት ለነጋሹ” ሆኗል፤ ለገበሬው የታሰበውን መሬት ወያኔ ወሰደው። የዱሮ ንጉሣዊ ገዢዎቿ ቤተ ሰቦች ስለነበሩ በቊጥራቸው ማነስ ምክንያት እነሱን በማር ግብር ለማጥገብና በሰላም ለመኖር ቀላል ነበረ። የዛሬዎቹ ገዢዎች ብሔረ ሰቦች ስለሆኑ እነሱን ሁሉ በሚሊዮን ዶላር ማጥገብ መራቆትን አስከትሏል።” ፕሮፌሰር ጌታቸው ኃይሌ (‘ዕርቅና ሰላም፤ የሕይወት ቅመም’ የካቲት 2006 ዓ.ም)

ወየኔዎች ወደ ሥልጣን ከመጡ በሗላ የአገሪቱን ሃብት ባገኙት አቅም እና ዘዴ ሁሉ በማራቆት ብቻ የተወሰኑ ሳይሆኑ የትግራይ ሕብረተሰብ በታሪክ ላይ የሚኖሮው ግንዛቤ የተጣመመ እንዲሆን አድረገውታል። በርከት ያሉ እንሰሳዎች በተለያዩ ምክንያቶች ሆን ብለው አጥቂዎቻቸውን ወይንም መሰሎቻቸውን ያታልላሉ። እንሰሳዎቹ በማታለል ዘዴ የሚኖሩበት ምክንያት የተለያዩ ምክንያቶች አሉዋቸው። ለምግብ፤ ወይንም እራሳቸው ከጥቃት ለመከላከል ሊሆን ይችላል።ይሁን እንጂ በተፈጥሮ እራሳቸውን እና ሌሎችን ሆን ብለው ለማታተለል/ለመዋሸት “የተሰሩ ፍጡሮች” ሰዎች ብቻ እንደሆኑ ያነበብኳቸው አንዳንድ የስነ ልቦና መጻሕፍቶች ይገልጻሉ።

ሙሉውን ለማንበብ እዚህ ይጫኑ

ምነው ሚኒስትር ዘነቡ ? –ከዲ/ን ዳንኤል ክብረት

$
0
0

zenebu Tadesse
ትናንት ማታ የሴቶች፣ ሕጻናትና የወጣቶች ጉዳይ ሚኒስትሯ ወ/ሮ ዘነቡ በትዊተር ገጻቸው ላይ ግብረ ሰዶምን በተመለከተ የጻፉትን ነገር ከምመለከት ወይ ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ ባይኖር ወይ እርሳቸው ሚኒስትር ባይሆኑ እመርጥ ነበር፡፡ የሴቶችና የወጣቶች፣ የሕጻናት ሚኒስትር ሆነው ግብረ ሰዶምን በመደገፍና የዑጋንዳን አዲሱን ሕግ በመቃወም መጻፋቸው ‹‹ይህቺ ሀገር ወዴት እየሄደች ነው›› ብዬ እንድጠይቅ አድርጎኛል፡፡ ከተወሰኑ ጊዜያት በፊት በአዲስ አበባ የተሾሙ የአሜሪካ አምባሳደር በኢትዮጵያ የግብረ ሰዶማውያን መብት እንዲጠበቅ እሠራለሁ ያሉትን አስታውሼ እኒህ ዲፕሎማት እውነትም ሠርተዋል ማለት ነው አልኩ፡፡

ከተወሰኑ ዓመታት በፊት የኤች አይ ቪ ኤድስ ጉባኤ በአዲስ አበባ ሲደረግ የእምነት ተቋማት መሪዎች ግብረ ሰዶምን በመቃወም መግለጫ ለመስጠት ተዘጋጅተው ወዲያው ነበር የተሠረዘው፡፡ ግብረ ሰዶማውያንን ተዋቸው ተብለው መግለጫቸው መሠረዙ፣ እነርሱም ያንን በዝምታ ማለፋቸው በሀገራችን ከተከናወኑ አሳዛኝ ተግባራት አንዱ ሆኖ እንዲመዘገብ አድርጎታል፡፡

zenebu Tadesse ዑጋንዳ ሕጉን ያወጣችው የግብረ ሰዶማውያንን ተግባር ለመከታተል፣ ለመቆጣጠርና ሕጋዊ ርምጃ ለመውሰድ ነው፡፡ የኢትዮጵያ ሕግም ግብረ ሰዶም ወንጀል መሆኑን ከዑጋንዳ ቀድሞ የደነገገ ነው፡፡ ምነው ሚኒስትራችን የግብረ ሰዶም ደጋፊ ሆነው ብቅ አሉ፡፡ ይህ ሕግኮ እርሳቸውንም የሚመለከት ነው፡፡ ግብረ ሰዶም በሀገሪቱ በድብቅ እየተድፋፋ ሕጻናትና ወጣቶችን እየቀጠፈ፣ ማኅበረሰባዊና ሃይማኖታዊ እሴቶቻችንን እያፈረሰ ነው፡፡ ሰውን ከተፈጠረበት ዓላማና ግብር ውጭ የሚያደርግ ነው ግብረ ሰዶም፡፡ እንስሳት እንኳን የማይፈጽሙትን የሚያስደርግ ነው ግብረ ሰዶም፡፡
ምዕራባውያን በራሳቸው ምክንያት የተነሣ የዚህ ሐሳብ ደጋፊም አቀንቃኝም ሊሆኑ ይችላሉ፡፡ እነርሱ የደገፉትን ሁሉ የመደገፍ ግዴታ ግን የለብንም፡፡ የእነርሱ ማኅበረሰባዊ ሥሪትና የእኛ ሥሪት ፈጽሞ አይገናኝም፡፡ በርግጥ ይህንን መሰል ርካሽ ነገሮችን መደገፍና ማቀንቀን ዓለም ዐቀፍ ተቀባይነትን ለማግኘት አቋራጭ መንገድ መሆኑ ይታወቃል፡፡ እኛ ግን ሚኒስትራችን የምንፈልጋቸው ለአሜሪካ ጉዳዮች አይደለም፤ ለኢትዮጵያ ጉዳዮች እንጂ፡፡
እርስዎ የተሾሙላቸው ሕጻናት፣ ሴቶችና ወጣቶች ሥራ፣ ንጹሕ ውኃ፣ የመኖሪያ ቤት፣ የጤና ተቋማት፣ ሰብአዊና ፖለቲካዊ መብቶች ቸግሯቸው እንጂ ግብረ ሰዶምነት አልቸገራቸውም፡፡ ግብረ ሰዶምነት የእነርሱ ማጥቂያ መሣሪያ እንጂ ክብርት ሚኒስትሯ የሚቀኙለትና የሚሟገቱለት አይደለም፡፡
ለሕጻናት፣ ለወጣቶችና ለሴቶች ያልተሠራ ብዙ አጀንዳ ባላት ሀገር፣ በዐቅም እጥረት በጤና ተቋማቱ የማይወልዱ እናቶች፣ በየጉራንጉሩ የሚወለዱ ሕጻናት፣ በየጫት ቤቱ ሥራ ፈትተው የሚባዝኑ ወጣቶች ያሏት ሀገር ግብረ ሰዶምን ጉዳዬ ብላ ማቀንቀኗ በዜጋ ላይ የሚፈጸም ስላቅ ነው የሚሆነው፡፡
እኔ ይህ መልእክት አሁንም የእርሳቸው ባይሆን እመርጣለሁ፡፡ ማብራሪያ እንደሚሰጡበትም ተስፋ አደርጋለሁ፡፡

ሚኒስትሯስ ምን ይላሉ?

ሚኒስትሯ ወ/ሮ ዘነቡ ለታድያስ አዲስ ዛሬ በ9 ሰዓት በሰጡት መግለጫ ‹‹ከልብ ነው ያዘንኩት፤ የእኔም አቋም አይደለም፤ የመንግሥትም አቋም አይደለም፤ ያየሁትም በትናንትናው ዕለት ነው፤ በሆነውም ነገር በጣም ነው ያዘንኩት፤ በተፈጠረው ነገር ሰብእናዬ ተጎድቷል፡፡ እስከ መጨረሻ ማጣራት ያለብኝን አጣራለሁ፡፡ ይህ በሀገሪቱ ሕግ ላይ የተቀመጠ ወንጀል ነው፡፡ ከእኔ ሰብእናም ጋር አይሄድም›› ብለዋል፡፡ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ሚኒስትር ዲኤታ አቶ ሽመልስም ‹‹አካውንታቸው ባልታወቁ ሰዎች ተጠልፏል›› ብለዋል፡፡

Viewing all 15006 articles
Browse latest View live