Quantcast
Channel: Ethiopian News | ዘ-ሐበሻ | Latest News Provider | News For All
Viewing all 15006 articles
Browse latest View live

“ስለአጼ ቴዎድሮስ እና አጼዮሐንስ መዝፈን የሚቻለው እነርሱ የሞቱለትን መሬት አሳልፈን ካልሰጠን ነው”–ኢንጂነር ይልቃል (ቪድዮ)

$
0
0

ባለፈው እሁድ በጎንደር ሰማያዊ ፓርቲ በጠራው ሰላማዊ ሰልፍ ላይ የፓርቲው ሊቀመንበር ኢንጂነር ይልቃል ጌትነት በተለይ ለወጣቶች ልብ የሚነካ ንግግር አድርገዋል። በንግግራቸው ከእንግዲህ በኋላ ስለአጼ ቴዎድሮስ እና አጼ ዮሐንስ መዝፈን የሚቻለው እነርሱ የሞቱለትን መሬት አሳልፈን ካልሰጠን ነው” ሲሉ ተደምጠዋል። ቪድዮውን ይከታተሉት።

Yilkal Getnet


አቶ አስራት ጣሴ ታሰሩ

$
0
0

(ዘ-ሐበሻ) የኢሕአዴግ አስተዳደር ለፕሮፓጋዳና ዜጎችን ለማስፈራሪያ የሠራውን “አኬልዳማ” ዶክመንታሪ ፊልም በኢትዮጵያ ቴሌቭዥን ከታየ በኋላ በፊልሙ ላይ አስተያየት ሰጥተዋል፤ መንግስትንም ዘልፈዋል በሚል የተከሰሱት የአንድነት ፓርቲ የምክር ቤት አባል አቶ አስራት ጣሴ ታሠሩ።

አስራት ጣሴ

አስራት ጣሴ


ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን ተጠቅመው በፊልሙ ላይ የተሰማቸውን አስተያየት ሰጥተዋል የሚባሉት አቶ አስራት በአዲስ ጉዳይ መጽሔት ላይ አስተያየታቸውን በመስጠታቸውና በዚህ ጽሑፍ ላይም መንግስት ላይ ዘለፋ አዘል ቃላት ተጠቅመዋል በሚል ፍርድ ቤት ቀርበው እንዲያስረዱ ትዕዛዝ የተላለፈባቸው ሲሆን፤ በዚህም መሠረት ዛሬ ፌብሩዋሪ 7 ቀን 2014 ዓ.ም ፍርድ ቤት ቢቀርቡም፤ የፌደራል የመጀመሪያ ፍርድ ቤቱም ለ7 ቀናት ያህል ታሰረው በቀጣይ ሳምንት እንዲቀርቡ የ እስር ት ዕዛዝ በማስተላለፉ አቶ አስራት ጣሴ ወህኒ ወርደዋል።

የዘ-ሐበሻ የአንባቢያን አስተያየት ይጠበቃል።

የብዕር ዕጢ –መናጢ

$
0
0

ከሥርጉተ ሥላሴ 07.02.2014 (ሲዊዘርላንድ – ዙሪክ)

Cry  ethiopiaዛሬ ልተርብ ሳይሆን ከልብ ሆነን በጎርባጣ መንገዶች ሊያስጉዙን የሚሽቱትን ፈንጋጣ ስሜቶች ከልብ ሆነን ባትኩሮት እንመረምር ዘንድ ፈለግሁኝ። ብላሽ – ዬቀለም ብዕር …. ሲባዛ መንፈስን ይበጥሳል ሲያንሰ ይሸረሽራል። ለመሆኑ ማንና ምን እንዲመራን እንፍቅዳለን? ናፍቆታችንስ ምንድን ነው?!
ህም! ቀዶ ጥገና ማድረግ ሽው አለኝ። ዖዬ! በምኞት ቀረ እንጂ የወጣልኝ የባይወሎጂና የኬሚስትሪ ትጉህ ተማሪ ነበርኩኝ። ያ .. ቢቀር ደግሞ ቢያንስ በደም ውስጥ የመርዝ መስኖ ቦይ ለከፈተ ባለ ዕጢ ብዕረ- በዝውውሩ ላይ ማዕቀብ ጥሎ ወደ ሆስፒታል ጎራ በማደረግ የተበከለውን ደም አጣርቶ በንጡህ ደም መተካት ግድ ይላል። የትውልዱ ንጹህ መንፈስ እጅ የሚያነሳ ወደርየለሽ ቅዱስ መንፈስ ሆኖ፤ የባለ ዕጢዋ ግን በካይ ሆነብን። ስለሆነም ግራ ቀኙን በንጽጽር በማቅረብ ለስሜታችንና ለፍላጎታችን የራቀውን ገፍቶ፤ የቀረበውን ማጣጣም ሸጋ ነው። ለነገሩ ባለ ዕጢዋ ብዕር ድሃ አይደለችም ምን አጥታ ዲታ ናት። መልክ ጥፉም አይደለችም ደም- ግቡ ናት። ነገር ግን ጣል ጣል የምታደርጋቸው ማላታይሎች ነገ ከመምጥቱ ቀድማ ችግር ጠሪ በመሆኑ ትፈተሽ፤ ትበርበር ተብሎ ብይን ተላላፈባት — እንዲህ ከወደ ሲዊዘርላንድ …..

Read Full Story in PDF/ሙሉውን ለማንበብ እዚህ ይጫኑ

የአንዷለም አራጌ የውሳኔ አሁንም ቀጠሮ ተራዘመ፤ ኢሕአዴግ 4 የአንድነት አመራሮችን ሊያስር መሆኑ ተሰማ

$
0
0

(ዘ-ሐበሻ) በኢትዮጵያውያን ዘንድ የዓመቱ ምርጥ ሰው በሚል የተሰየመው ወጣቱ ፖለቲከኛ አንዷለም አራጌ በካንጋሮው ፍርድ ቤት ዕድሜ ልክ ዕስራት እየተፈርደበት መሆኑ ይታወሳል። ወጣቱ ፖለቲከኛ ለሰበር ሰሚ ችሎት አቤቱታ ያቀረበ ሲሆን ለውሳኔ ከተቀጠረ በኋላ አሁንም እንደዚህ ቀደሙ ቀጠሮው መራዘሙን የዜና ምንጮች ለዘ-ሐበሻ ጠቁመዋል።
Andualem aragie
አቶ አንዷለም አራጌ የእድሜ ልክ እስራት ተፈርዶበት ወህኒ እየተሰቃየ ቢሆንም “የእኔን መታሰር ተቃዋሚዎች ሊጠቀሙበት አልቻሉም” ሲል መናገሩ አይዘነጋም። ዛሬ ፍርድ ቤት መቅረብ የነበረበት አንዷለም በዳኞች የተለመደ ምክንያት ቀጠሮው ለመጋቢት 8 ቀን 2006 እንዲተላለፍ ተወስኗል። ዛሬ አንዷለም ላይ ምን ይወሰን ይሆን የሚለውን ለማየት በርካታ ሰዎች ስድስት ኪሎ በሚገኘው ጠቅላይ ፍርድ ቤት ታድመው እንደነበርም የደረሰን መረጃ ያመልከታል።

Daniel Tefera የፍኖተ ነፃነት ጋዜጣ ዘጋቢ ነብዩ ሃይሉ እንደዘገበው ኢህአዴግ አቶ ዳንኤል ተፈራን ጨምሮ አራት የአንድነት አመራሮችን ለማሰር መዘጋጀቱ ተጋለጠ። በዘገባው መሠረት ወጣቱ ፖለቲከኛና ደራሲ ዳንኤል ተፈራን ጨምሮ 4 አመራሮችና አባላት እንዲታሰሩ ኢህአዴግ ወስኗል፤ የክስ ቅድመሁኔታዎች በፍርድ ቤት መጠናቀቃቸውን ታውቋል፡፡

የፍትህ ሚ/ር ምንጮች እንዳስታወቁት በኢህአዴግ ጽ/ቤት ትዕዛዝ ክስ እንዲከፈትባቸውና እንዲታሰሩ የተወሰኑት የአንድነት አባላት በርካታ ናቸው፡፡ ሆኖም የመጀመሪያው ዙር ክስና እስር በ4 አመራሮችና አባላት ላይ ያነጣጠረ ነው ይላል የፍኖተ ነፃነት ጋዜጣ ዘገባ።

[የሚኒሶታው መድሃኔዓለም ቤ/ክ ጉዳይ] የሰንበት ትምህርት ቤቱ ሕዝብ ግንኙነት ቅጥፈት ሲጋለጥ

$
0
0

ከመ/ር ሰናይ ገ/ህይወትና ቴዎድሮስ

በቅድሚያ ዘሀበሻ ድረ ገጽ ሁለቱንም ወገኖች ህሳባቸውን ለማደመጥ የምታደርገውን ጥረት አደንቃለሁ። ሆኖም ግን ሃገር ቤት ካለው ሲኖዶስ ጋር እንዲቀላቀል ከሚፈልገው ወገን የሚሰጠውን ሃሰተኛ ዘገባ ዘሀበሻ ለሚዛናዊነት በሚል በቀጥታ ከማስተናገድ ይልቅ ቆም ብላ ብታስብበት መልካም ነው እላለሁ። ዛሬ ለመጻፍ ያነሳሳኝ ትናንት በዚሁ ድረገጽ ላይ የታተመውን የቤዛ ኩሉ ሰንበት ትምህርት ቤት የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ በኢሜይል እና በተለያዩ ዘዴዎች የበተነውን መግለጫ ይመለከታል። ዘገባው እጅግ ሃሰት እንደሆነና ሁሉም ነገር በፍርድ ቤት ውድቅ እንደሆነ የዘገበበትን ቅጥፈት ለማጋለጥ ነው ወደዚህ ብቅ ያልኩት።

ከአንድ የሰንበት ትምህርት ቤት አባል ወይም መሪ ነኝ ከሚል ሰው የማይጠበቅ ቅጥፈት ተፈጽሟል። ይህም እግዚአብሔርን ያሳዝናል። የፍርድ ቤቱ ውሳኔ ዶክመትን እንደሚከተለው አያይዣለሁ፤ አንባቢዎች እንደሚፈርዱም ይህ ያሳያል።
order for trial (1)_Page_1
ልብ ብላችሁ ካነበባችሁት በመጨረሻው መስመር ላይ “ከማርች 10 በፊት የሚስማሙ ከሆነ” ይላል። ይህ ማለት የሚጠራው ጠቅላላ ጉባኤ ነው። ይህን ደግሞ ዘሀበሻም ቀድሞ ዘግቦታል። የሰንበት ትምህርት ቤቱ እንዳወራው ቅጥፈት ፍርድ ቤቱ በጽሁፍ ባወጣው ትዕዛዝ ላይ ስለ ቦርዱ፣ ስለገንዘቡ፣ ወዘተ… የሚያወራው የለም። የእግዚአብሄርን ስም እየጠሩ ቅጥፈት ያሳፍራል።

እኔን የገረመኝ ቤተክርስቲያኑን በተመለከተ ይህን የመሰለ ሃሰተኛ ወሬ ሰንበት ትምህርት ቤቱ ሲያሰራጭ ደብረሰላምን የሚመራው ማን ነው? የሚለውን ጥያቄ ውስጥ ይከታል።

ውድ ወገኖች፤ እውነቱ ይኸው ነውና በቀጣዩ የአጠቃላይ ጉባኤ ላይ በመገኘት ለውሳኔ እንዘጋጅ። ቤተክርስቲያናችንን የምናድነው ያኔ ነው።

ተጨማሪ አስተያየት ቴዎድሮስ ከተባሉ የቤተክርስቲያኑ አባል የተሰጠ ይከተላል

የሜኖሶታ: ደብረሰላም: መድሀኒአለም: ቤተክርስቲያንን: የውስጥ: ችግር: ለመፍታት: በ02/05/2014 የነበረው: የፍርድ: ቤት: ውሎ: እና በዳኛዋ: የተሰጠ: ያልተዛባ: ውሳኔ: እንደሚከተለው: ነው።

በመጀመሪያ: ከላይ: በተጠቀሰው: ቀን: የአቶ: ጥበቡ: እና: አቶ: ጥበቡን: አወረድኩ: የሚለው: ቦርድ: በጠበቆቻቸው: አማካኝነት: ጉዳያቸውን: አቅርበው: በተከበረው: ፍርድ: ቤት: የተከራከሩ: ሲሆን፣ የተከበሩት: ዳኛ: ነገሩን: ከነመረጃቸው: ካዩ: ቡሃላ: የሚከተለውን: አጠቃላይ: መመሪያ: ለሁለቱም: ወገን: ጠበቆች: ሰጥተዋል።
1፣ አጠቃላይ: የአባላት: ስብሰባ: ለ02/23/2014 እንዲደረግ (ይህ: የተወሰነው: አቶ: ጥበቡ: ባቀረቡት: የ 355: የአባላት: ግልፅ: እና: እውነተኛ: ፊርማ: ነው።)

2፣ በ 02/23/2014: በሚደረገው: አጠቃላይ: የአባላት: ስብሰባ: ጊዜ: አባላቱ: ማድረግ: የሚፈልገውን: ማንኛውንም: አይነት: አጀንዳ: አንስቶ: የማፅደቅና: የመጣል: ፍፁም: ሙሉና: ያልተገደበ: መብት: አለው።

3፣ ምክትል: ሊቀመንበሩ: ለጊዜው: የሚሰሩ: ስራዎችን: ያከናውናል።

4፣ የባንክ: አካውንቱ: ከመደበኛ: ክፍያዎች: ውጪ: መጠቀም: ወይም: ማንቀሳቀስ: ፈፅሞ: አይቻልም።

5፣ ይህ: ጉዳይ: በአጠቃላይ: ስብሰባው: ካልተፈታ: የተከበሩት: ዳኛ: በ 03/02/2014: ነገሩን: አይተው: የፍርድ: ሂደቱ: ይቀጥላል: ማለት: ነው።

እነዚህ: ናቸው : እንግዲህ: አጠቃላይ: ውሳኔዎቹ።
ማንኛውም: ሰው: እነዚህን: የዳኛ: መመሪያዎች: ከሁለቱም: ጠበቆች: ማግኘት: ይችላል። በጣም: የሚገርመው: ይህ: የተከበሩት: ዳኛ: ውሳኔ: በኢትዮጽያ: ሲኖዶስ: ይሁን: የሚሉትን: ጠበቃ: እና: ደንበኞቿን: ለምን :እንደሚያስፈራቸውና: እንደሚያስደነግጣቸው: አይገባንም። በተለይ: ለምን: አጠቃላይ: ስብሰባን: እንደጦር: እንደሚፈሩት: ሲታይ: በጣም: ይገርማል።
ይህ: አሜሪካ: ነው። ማንም: የማንንም: መብት: የሚገድብበት: መብት: የለውም። በተጨማሪም: የሜኖሶታ: መድሀኒያለም: ቤተክርስቲያን: የህዝብ: እንጂ: የጥቂት: ሰዎች: አይደለም። እናም፣ እንደራሳችሁ: የግል: ቤትና: ንብረት: መቁጠራችሁን: ትታችሁ: የህዝቡን: ድምፅ: ያለምንም: ቅድመሁኔታ: በፍፁም: ትህትናና: አክብሮት: ስሙ።
debereselam Minnesota

የቤተ መንግስት ዙሪያ መፈክሮች!

$
0
0

ከቤታቸው ሽፈራው

ድሮ በቤተ መንግስት ዙሪያ ሳልፍ የሆነ ነገር ይጫጫነኝ ነበር፡፡ በቃ! ቤተ መንግስቱ አንዳች ጣኦት የሚመለክበት፣ አሊያም ባዕድ ነገር የሞላው አድርጌ ስለምቆጥረው በአካባቢው ማለፍ ይከብደኝ ነበር፡፡ አሁን ግን ቤተ መንግስቱ አጥር ላይ የተሰቀሉት ጽሁፎች ይህን ድባብ በትንሹም ቢሆን ቀይረውልኛል፡፡ እነዚህ መፈክሮች ሁሌም ያስፈግጉኛል!
meles fun
የአቶ መለስ ሞት ከተነገረ በኋላ እንደ ማንኛውም የአዲስ አበባ ነዋሪ ቤተ መንግስት የመግባት እድል ባገኝም ለመግባት ደስተኛ አልነበርኩም፡፡ አንድ ቀን እንደምንም ደፍሬ በለቅሶ ስም ይህን የምጠላውን ቤተ መንግስት ለመጎብኘት ወንድሜን ሳማክረው ‹‹መለስን ያልሰራውን ሰራ እያሉ የሚዘሉ የሚፈርጡትን ካድሬዎች ስናይ ሳቃችን ያመልጠናል፡፡ ይቅርብን!›› የሚል ጠቃሚ ምክር ስለለገሰኝ ቤተ መንግስቱን ሳላየው ቀርቻለሁ፡፡

በእርግጥ ቤተ መንግስት ውስጥ ለማስመሰል ሲዘሉ የነበሩትን ካድሬዎች በኢቲቪ መስኮትም አይቼ ሆዴን ጨብጩ ስቄያለሁ፡፡ የፈረንሳይ ልጆች ደግሞ ይህን የካድሬዎች የለበጣ ለቅሶ ‹‹አሸባሪ በለኝ፣ አንድ ለአምስት ጠርንፈኝ፣ የምርጫ ኮረጆ ልገልብጥልህ፣ ትምክተኝ ብለህ ስደበኝ፣ ተንበርካኪ በለኝ፣ ልማታዊ በለኝ፣ በይቅርታ አስፈርመኝ፣…….›› እያሉ በሽሙጥ ሲያለቅሱ እንደልባችን እየሳቅን የምንታደምበትን ቤተ መንግስት (ፈረንሳይ) መረጥን!

ቤተ መንግስት ባንገባም ስለ አቶ መለስ የሚባሉትን ነገሮች ከአልቃሾቹ እኩል በኢቲቪና ጎዳና ላይ እንከታተላለን፣ እናነባለን፡፡ በዚህ ረገድ ቤተ መንግስቱ ዙሪያ የተሰቀሉት መፈክሮች ቀዳሚዎቹ ናቸው፡፡ በተለይ የመጀመሪያው ሰሞን ላይ እነዚህን ጽሁፎች ስመለከት በሚቀፈኝ መንገድ እንደ እብድ ገጥጨበታለሁ፡፡ በርካቶችም ልክ እንደ እኔ ሲስቁ ተመልክቻለሁ፡፡

ከአራት ኪሎ በኩል በሚገኘው የቤተ መንግስቱ ጫፍ ላይ ‹‹ጀግና አይሞትም!›› የሚል መፈክር ከአቶ መለስ ፎቶ ጋር ተሰቅሏል፡፡ ይህኔ ከአርጀንቲና ቮልቪያ፣ ከዛም ኩባ፣ ከደቡብ አሜሪካ ወደ አፍሪካዋ ኮንጎ በጎሳ፣ ዘውግ፣ ሀይማኖት፣ ቀለም የማይመሳሰሉትን ዜጎች ከጭቆና ለማውጣት የባዘነውን ‹‹ቼ››ን አሰብኩት፡፡ ሁችሚኒ፣ ማርቲን ሉተር ኪንግ፣ ቴዎድሮስ፣ በላይ፣ አቢቹ፣ አሉላ፣ አብዲሳ አጋ…….ህዝብን በጎሳና ዘውግ ሳይከፋፍሉ መሞታቸውን አስታወስኩ! ታዲያ የትኛው ጀግና ነው የማይሞተው? ነው የጀግና ትርጉም ተቀየረ? እያልኩ በማሰላሰል ላይ እያለሁ ሁለተኛውን መፈክር ተመለከትኩ፡፡

‹‹ዓለም ያጣችው ምርጥ መሪ!›› የሚል ነው፡፡ ዓለም ቤተ መንግሰቱ ነው? አዜብ መስፍን ናቸው? ቻይና ነች? እያልኩ ከራሴ ጋር ስቀልድ የመጀመሪያውን መፈክር በሙሉ ድምጽ የሻረ ሌላ መፈክር ተሰቅሎ አየሁ፡፡ ይህኛው ጉደኛ መፈክር ‹‹የጀግና እረፍቱ ሞቱ ነው!›› ይላል፡፡

ይህ ለሌላ ሰው ነው እንዳልል የአቶ መለስ ፎቶ ተለጥፎበታል፡፡ አዎ! ለመጀመሪያ ጊዜ ያንን በዓድ መንገድ ረዥም ሳቅ ሳቅኩበት፡፡ በቤተ መንግስቱ አስቂኝ መፈክሮች መሰረት 20ና 30 ሜትር ውስጥ ዘላለማዊ የነበረ ‹‹ጀግና›› ለእርፍት ወደ ሰማይ ቤት ያመራል፡፡ በዛን ሰሞን ወይዘሮ አዜብ መስፍን ቤተ መንግስቱን የራሳቸው ንብረት አድርገው ‹‹እዩት የእኛን ቤት፣ ይህ ነው የእኛ ቤት፣….›› እያሉ ሲያስጎበኙ በጣት የሚቆጠሩ ሰከን ያሉ ካድሬዎች ሳይቀሩ ‹‹እኒህ ሴትዮ ጭራሹን ባሰባቸው›› ብለው አሽሟጥጠዋል፡፡ እኔም ምን አልባት እነዚህ ጽሁፎች በአዜብ መስፍን ትዕዛዝ የተሰቀሉ ቢሆኑስ? የሚል ሀሳብ መጣብኝ፡፡ ደግሞ ‹‹ቤቴ ነው!›› ከሚሉት ቤተ መንግስት አጥር ድረስ ይቅርና ሳውዲና ስይዘርላንድ ድረስም በአገሪቱ ገንዘብ የሚያንጋጉዋቸው ታማኞች እንዳሏቸው አውቃለሁ፡፡ ከወይዘሮ አዜብ ጋር ቤተ መንግስቱ ውስጥ ሲያለቅሱ የነበሩትን ግራ አጋቢ ካድሬዎች አስታወስኩ! ግራ የተጋቡ ካድሬዎች በበዙበት መፈክሮቹም የትየለሌ ናቸው!

አንዳንዶቹ ከጎኑ ደግሞ ምን አልባትም አቶ መለስ አምስትና ስድስት አመታቸው የተነሱት ፎቶ ግራፍ አብሮ ተለጥፏል፡፡ አቶ መለስ በአምስትና ስድስት አመታቸው ጀምረው ነው ኢትዮጵያን ሲመሩ የኖሩት ከሚል እሳቤ የመጣ መሆን አለበት፡፡ ይህኛው ደግሞ ከሀይማኖት አባትነታቸው ይልቅ ካድሬነታቸው ከሚያመዝነው ‹‹የሀይማኖት አባቶች›› የተበረከተ ይሆናል፡፡ ልክ እየሱስ ክርስቶስ ልጅ ሆኖም ጌታ እንደነበረው ማለት ነው፡፡

አሁን የቤተ መንግስቱን አጥር እያጋመስን ነው፡፡ ሌላ መፈክር! ‹‹አንተ ብትሞትም ራዕይህ ይቀጥላል!››፡፡ ይህኛው እረፍትም ሆነ ዘላለማዊነት የለውም፡፡ በእነዚህ መፈክሮች ተቃርኖ ሳቄን ሳላባራ ማዶ ላይ በላቸው ግርማ ከአንዲት አሮጊት፣ ሸገር ብሎ ደግሞ ከወት ጋር ተንጋሎ እየሳቀ ተመለከትኩት፡፡ እነዚህ መፈክሮች አይደለም አንተን? ሌላ ቀን ግርማቸው በደረቁ ነው የሚስቀው፤ ቤተ መንግስት ፊት ለፊት ያለው ግርማቸው ግን ሁሌም ከምር ይንፈረፈራል! እኔም ተክዤ፣ ተናድጄ፣ ደክሞኝ ውዬም ቢሆን የምስቀው ቤተ መንግስት ስደርስ ነው፡፡
የገረመኝ የኃይሌ ጉዳይ ነው፡፡ ብዙዎቹ በሚስቁበት ጎዳና ሁሌም አረቄውን ከፊቴ አጋድሞ ይሮጣል፡፡ ከፊቱ ላብም ይሁን እንባ ብቻ የሆነ ነገር ይታየኛል፡፡ እምባ መሆን አለበት፡፡ የመፈክሮቹን ተቃርኖ የተመለከተማ (በአረቄ) ስካር የተጻፉ ስለነሆናቸው ቢጠረጥር አይፈረድበትም፡፡ መጠርጠር ነው!

እውን ሻዐቢያ እና ህወሀት ተጣልተዋልን?

$
0
0

(ሁኔ አቢሲኒያዊ)

ማማ እና የሾላ ወተት ሁለቱም ወተት ናቸው የሚለያቸው ነገር ቢኖር ማማ ማማ መባሉ ሲሆን ሾላ ደግሞ ሾላ መባሉ ነው እንደዚሁ ህወሀት እና ሻዐቢያም የስም እንጂ የይዘትም ሆነ የአላማ ልዩነት የሌላቸው ጸረ ኢትዮጵያዊ ናቸው፡፡ ፀረ ኢትዮጵዊ መሆናቸው ሀቅ እና ምስጢር ያልሆነ ነው ይልቁንስ በዚህች አነስተኛ ጦማር ማሳየት የፈለኩት ሻዐቢያን አምነው የኢትዮጵያን ፖለቲካ ለመቀየር ከኢሳያስ ጋር ስለተወዳጁ ወገኖቻችን ጉዳይ ነው።
isayas afewerki
ምርጫ 2002 በተቃረበበት ወቅት በኢህአዴግ ማዕከላዊ ኮሚቴ ቀረበ የተባለው እና በፊታውራሪ ህወሀቶች ጭምር ድጋፍ ተሰጥቶት ነበረ የተባለው የስልጣን እንልቀቅ ጥያቄ ውድቅ የተደረገው እኛ ስልጣን ከለቀቅን ሻዐቢያ በእጅ አዙር ሀገሪቷን ሊመራት ስለሚችል ስልጣን መልቀቃችን ሊታሰብ የማይችል ነው ሲሉ በተላላኪ ጋዜጠኞቻቸው በኩል አስነገሩ ብዙሀኑ ምስኪን የግል ጋዜጦችም ይህንን ጉዳይ አንስተው ከሁሉም ጆሮ እንዲዳረስ አደረጉ፡፡ ይህ ሁኔታ ወያኔ ኢህአዴግን በሁለት መንገድ ተጠቃሚ አደረገው እነርሱም፡-

1. ሻዐቢያ እውነትም ፀረ ኢትዮጵያዊ ነው ኢህአዴግ ከወደቀ ደግሞ ሻዐቢያ ኢትዮጵያን ይቆጣጠራል የሚለው አስተሳሰብ ውስጥ ብዙሀኑ ኢትዮጵያዊ ጥልቅ ብሎ እንዲገባ ያስቻለ ሲሆን

2. በሌላ በኩል ዲያስፖራ ላይ የመሸጉ የፖለቲካ ፓርቲዎች እነ ኦነግ ከኢሳያስ ጋር ተለጥፈው ለምን ውጤታማ ሳይሆኑ ቀሩ እንኳን ብለው ሳያጤኑ ሻዐቢያ የወያነ ጠላት ስለሆነ ለእኛ እና ለሰፊው የኢትዮጵያ ህዝብ ብቸኛው ኢትዮጵያን ነጻ የማውጫ መንገድ አስመራ ላይ መክተም ነው ብለው አውጀው የማይታመነውን ኢሳያስን አምነው አስመራ ከተሙ፡፡

እነዚህ ሁለት ከላይ የጠከስኳቸው ሁለት አብይት ጉዳዮች ወያኔን ተጠቃሚ ያደረጉ እንዲሁም የኢትዮጵያን ፖለቲካ ፓርቲዎች እንዲዳከሙ ምክንያት የሆኑ ጉዳዮች ነበሩ፡፡

– እውን ህወሀት እና ሻዐቢያ ተጣልተዋል ወይስ ጥላቸው ለሚዲያ እና ለህዝቡ ጆሮ ብቻ ነው?
- ኤርትራ የከተሙ ፓርቲዎችስ ስለምን ውጤታማ አልሆኑም?
- እነዚህን ጥያቄዎች ለመመለስ እስኪ በቅድሚያ ይህንን ሀሳብ በአዕምሯችን እናሰላስለው
- ሻዐቢያ አሰብ የራሱ እንዲሁም የኤርትራ ንብረት እንደሆነ ያምናል
- ህወሀትም አሰብ የኤርትራዊያን ንብረት እና ሀብት ነው ብሎ ያምናል

በተቃራኒው ብዙዎቹ ተቃዋሚ ፓርቲዎች አሰብ የኢትዮጵያ ነው አልፎም ተርፎ የኤርትራን መገንጠል የማይደግፉ ናቸው ታድያ የኛ ፓርቲዎች እንደምን ብለው ነው ኢሳያስን አምነው አስመራ ላይ የከተሙት እውን ኢሳያስስ አሰብ የኢትዮጵያ ናት ብለው የሚሰብኩት ተቃዋሚዎች ይሻሉታል ወይስ ኤርትራ ነጻ ሀገር ነች አሰብም የኤርትራ ነች የሚለው ወያኔ?

ህወሀት እና ሻዐቢያ በስልጣን ላይ ለመቆየት የማይገድሉት ሰው የማይቆፍሩት መሬት የለም በኤርትራ ሪፈረንደም ወቅት እስካሁን ትርጉሙ ሊገባኝ ባልቻለ መልኩ የመለስ ዜናዊ እናት ኢትዮጵያ ሬድዮ ላይ ቀርባ ኤርትራዊያን ነጻ ሀገር ስለሆኑ እንኳን ደስ ያላቹህ ያሉ ሲሆን ነጻነቱም እንደሚገባቸው ተናግረዋል ነገር ግን ከአመታት በኋላ እነዚሁ የህወሀት ባለስልጣናት እናቶቻቸውን ሁሉ ያስደሰተውን መልካ ግኑኝነት ወደኋላ ብለው የኢትዮ-ኤርትራ ጦርነት ተፈጠረ ተባለ እና ከ 78000 በላይ ወጣት ኢትዮጵያዊያን እንዲፈጁ ተደረገ ይህም ጠንካራ የነበረውን የኢትዮጵያ ወጣት እሳት ውስጥ የማገደ ብሎም የቀረው ጠንካራ ወጣት እንዲሰደድ ምክንያት የፈጠረ ሴራ ነበር በጦርነቱ መሀል መሪዎቻችን ምን ያደርጉ እንደነበር በቅርቡ ዊኪሊክስ ላይ ካየነው በኋላ ጦርነቱ የድንበር ሳይሆን ወጣት የማስፈጃ እንደነበር ለመረዳት ተችሏል፡፡
በአንድ ወቅት መሳሳት ልማዱ የሆነው ስብሀት ነጋ አዳልጦት በብሄራዊ ቲያትር የኤርትራ እና የኢትዮጵያ ህዝቦች እጅግ የሚዋደዱ እና ወንድማማች ህዝቦች ናቸው ካለ በኋላ ኤርትራን የሚወር አንድ ሀገር ቢመጣ ቀድመን ጦራችንን ከኤርትራ ወንድሞቻችን ጋር እናሰልፋለን በማለት መናገሩን ለሚያስታውስ ግለሰብ ግን ህወሀት እና ሻአቢያ ተጣልተዋል የሚለው ብሂል እውነታነቱ ለኢቲቪ ተመልካች እንጂ ማሰብ ለሚችል ሰው መራር ቀልድ ነው የሚሆነው፡፡

ከሰሞኑ ደግሞ በኤርትራ የሚገኙ የት.ብ.ዴ.ን አባላት ነጻ እናወጣዋለን ያሉትን የትግራይ ህዝብ ነጻ ከማውጣት ይልቅ ወታደሮቻቸው አስመራ ውስጥ ኬላ ጠባቂ እንደሆነ በማህበራዊ ድህረ ገጾች አነበብኩ የተጠበኩት ነገር ስለሆነ ባይገርመኝም የወያኔን እድሜ እያራዘመን እንደሆነ ሲገባኝ ግን አዘንኩኝ በነገራችን ላይ የኤርትራ ተቃዋሚዎችንም ሰብስቦ በመያዝ ረድፍ ህወሀትም ለሻዐቢያ ውለታ እየሰራ እንደሆነ ጠጋ ብሎ የሻዐቢያ ተቃዋሚዎችን ያነጋገረ ግለሰብ የሚረዳው ሀቅ ነው፡፡

ስለ ሻአቢያ ደህንነት ከህወሀት በላይ የሚጨነቅ ሊኖር ይችላል ብሎ ማሰብ የዋህነት ነው ሻዐቢያ ማለት ለህወሀት ዘብ ነው ህወሀት ለሻዐቢያም እንደዛው እናም ከሻዐቢያ ጋር በመወዳጀት ወያኔን እንጥላለን ሀገራችንንም ነፃ እናወጣለን ማለት ሞኝነት ስለሆነ ቆም ብለን አካሄዳችንን ማሳመር ይኖርብናል፡፡

ሁኔ አቢሲኒያዊ
ከፒተርቦሮው ዩ.ኬ

“ሙያው ያስከበረኝን ያህል ስላከበርኩት፤ ዛሬ ለብዙ ወጣት ሴት ተዋንያኖች መውጣት ምክንያት ሆኛለሁ”–ዓለምፀሐይ ወዳጆ

$
0
0

በጥበብ ሙያዋ ከፍተኛ አክብሮት የሚሰጣት አርቲስት ዓለምፀሐይ ወዳጆ ከወደ አውስትራሊያ ከሚሠራጨው ሲቢኤስ ራድዮ ጋር ባደረገችው ቃለምልልስ “ሙያው ያስከበረኝን ያህል ስላከበርኩት፤ ዛሬ ለብዙ ወጣት ሴት ተዋንያኖች መውጣት ምክንያት ሆኛለሁ” አለች። በጥበብ ሥራዎቿ አንቱታን ያገኘቸው ዓለምፀሐይ ወዳጆ ከጋዜጠኛ ካሳሁን ሰቦቃ ጋር ቃል የተመላለሰችበት የድምጽ ዘገባ ክፍል 1 እንደሚከተለው ቀርቧል፦

“ሙያው ያስከበረኝን ያህል ስላከበርኩት፤ ዛሬ ለብዙ ወጣት ሴት ተዋንያኖች መውጣት ምክንያት ሆኛለሁ” – ዓለምፀሐይ ወዳጆ


“የአቶ አስራት ጣሴ እስር ፖለቲካዊ እንደምታ ያለው ይመስላል”–አቶ ተክሌ በቀለ

$
0
0

(ፍኖተ ነፃነት) አንድነት ፓርቲ የኢትዮጵያ ቴሌቪዥንና ሬዲዮ ድርጅት “አኬልዳማ” በሚል ርዕስ ያቀረበው ዶክመንተሪ ፊልም የፓርቲያችንን ስም ያጎደፈ ነው በሚል የከፈተው ክስ በሂደት ላይ እያለ ዶክመንተሪ ፊልሙ በድጋሚ በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን መታየቱን በማውገዝ በአዲስ ጉዳይ መጽሔት የፃፉትን የግል አስተያየት ተከትሎ “በፍርድ ቤቱ ላይ ዘለፋ” ሰንዝረዋል በሚል ለእስር መዳረጋቸው ፖለቲካዊ አንድምታ እንዳለው ተጠቆመ፡፡

አስራት ጣሴ

አስራት ጣሴ


የአቶ አስራት የህግ ጠበቃ አቶ ተማም አባ ቡልጉ በትላንትናው ዕለት ጥር 30 ቀን 2006 ዓ.ም በዋለው ችሎት በቅድሚያ የስነ -ስርአት ጥያቄ ለማቅረብ እንዲፈቀድላቸዉ በመጠየቅ የሚከተለዉን የስነ-ስርአት ጥያቄ አቅርበዋል “ደንበኛዬ የተጠሩበት መንገድ ላይ የስነ-ስርአት ጥያቄ አለኝ ፡፡ በችሎት ያልነበሩ ሰውን በሌላ ቦታና መጽሔት በሰጡት አስተያየት በፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሕግ ቁጥር 480 ሊጠየቁ አይገባም” ብለዋል ፡፡ አስከትለውም የተጠቀሰውን አንቀፅ ቃል በቃል በማንበብ በአንቀፁ ሊጠየቁ የሚገባቸው በችሎት ተገኝተው የፍርድ ቤቱን ሂደት ያወኩ እንደሆነ ብቻ መሆኑን በማስመር “የኔን ደንበኛ ከውጪ ተጠርተው መጠየቅ አይችሉም፤ ደንበኛዬ ብዚህ ችሎት ተማጋች አይደሉም በስፍራውም አልነበሩም፤ ጥፋት ሰርተዋል ቢባል እንኳን በዚህ አንቀፅ ሊጠየቁ አይገባም ፡፡” በማለት ተከራክረዋል፡፡

ሆኖም የጠበቃውን መከራከሪያ ግልጽ ባልሆነ ምክንያት ፍርድ ቤቱ ባለመቀበሉ አቶ አስራት ስለተጠሩበት ጉዳይ ጠበቃ ተማም ምላሽ ሰጥተዋል፡፡ በምላሻቸውም “ደንበኛዬ ይህን ችሎት በተለየ በሚመለከት አልፃፉም፤ አቶ አስራት የገለፁት አጠቃላይ እውነታን ነው፡፡ ኢህአዴግ ስላቋቋማቸው ፍርድ ቤቶች ነው በአጠቃላይ የጻፉት፡፡ በህገ መንግስቱ አንቀፅ 29 መሰረት ስለፍርድ ቤትም ሆነ በማንኛውም ጉዳይ ላይ መጻፍም ሆነ አመለካከት የማበጀት መብት አላቸው፡፡” በማለት ምላሻቸውን አቅርበዋል፡፡ ፍርድ ቤቱም ውሳኔውን በ8፡30 እንደሚያቀርብ ቀጠሮ ሰጠ፡፡

ከሰአት በኋላ በችሎቱ ቀጠሮ መሰረት የቀረቡት አቶ አስራት ጣሴ ባልተጠበቀ ሁኔታ ጥፋተኛ ተብለው ለቅጣት ውሳኔ ከሰባት ቀናት በኋላ እንዲቀርቡ እስከዛውም በእስር እንዲቆዩ ተወስኖባቸዋል፡፡

ከውሳኔው በኋላ ለፍኖተ ነፃነት አስተያየታቸውን እንዲሰጡ የተጠየቁት የአንድነት ፓርቲ ተቀዳሚ ፕሬዝዳንት አቶ ተክሌ በቀለ እስሩ ፖለቲካዊ እንድምታ ሊኖረው እንደሚችል ተናግረው፣ “አቶ አስራት ጣሴ ፓርቲዎችን በማቀራረብ ረገድ የሚያደርጉት እንቅስቃሴ ኢህአዴግን አስደንግጦታል እስሩም የአስራትን አስተዋፅኦ ለመገደብ የተደረገ ይሆናል፡፡” የሚል ምላሽ ሰጥተዋል፡፡ አያይዘውም በቅርቡ በአንድነት ብሔራዊ ምክር ቤት ና ስራአስፈፃሚ የፓርቲዎችን የውህደት ድርድር እንዲመሩና የፓርቲውን አማካሪ ምክር ቤት እንዲያቋቁሙ ኃላፊነት እንደተሰጣቸውም ተናግረዋል፡፡

ምንጭ፡ ፍኖተ ነፃነት ጋዜጣ

ኢትዮጵያዊነት –”የለህም ይሉኛል፤ እውነት የለሁም ወይ?”

$
0
0

ከመስፍን ነጋሽ (ጋዜጠኛ)
(የቀድሞው አዲስ ነገር ጋዜጣ አዘጋጅ)

(ጋዜጠኛ መስፍን ነጋሽ)

(ጋዜጠኛ መስፍን ነጋሽ)

ከማንነት ጋራ የተያያዙ ጥያቄዎች፣ ሙግቶች፣ በተቃራኒውም አስቀያሚ ሐሳብ አልባ ስድድቦች ሰሞኑን በርከትከት ብለዋል። ጥያቄዎቹና ሙግቶቹ መኖራቸውን አጥብቄ እደግፈዋለሁ። በእኔ እይታ አብዛኞቹ ምልልሶች ወይም ሙግቶች በመሠረቱ አዲስ ጭብጥም ሆነ መከራከሪያ አላቀረቡም። ቢሆንም የነበረውንም ቢሆን በአግባቡ በተደጋጋሚ እያነሱ ሐሳብ መለዋወጡ ጠቃሚ ነው፤ ሙከራው ቢያንስ እርስ በርስ መተዋወቅን ይጨምራል፤ አልፎም አዲስ ሐሳቦችን ለማፍለቅ እድል ይሰጣል።

የማነ ናግሽ ኢትዮጵያዊ የሚባል ማንነት የለም፤ ያለው በብሔረሰብ ላይ የተመሰረተ ማንነት ብቻ ነው የሚለውን ሐሳብ በትግሪኛ ጽፎት ተመልክቼ ነበር። ኃላም ራሱ ወደ አማርኛ እንደመለሰው ይህን ጽሑፍ ወደማጠናቀቁ ስቃረብ ተመልክቻለሁ። በመሠረቱ ሐሳቡ አዲስ አይደለም። በየማነ አስተያየት መነሻነት ሌሎችም አመለካከታቸውን አካፍለዋል፤ ጥቂቶቹን በሚገባ አንብቤያለሁ። በሒደቱ የታየው ጉዳዩን ከመመርመር ይልቅ ተናጋሪውን የማጥቃት ስልት ጠቃሚ ስላልሆነ ወደዚያ አንመለሰም። በሐሳቡ ላይ ግን አስተያየቴን ላካፍል።

1. ስለማንነት እንደመነሻ

ሁልጊዜም ከጥንቱና ከስሩ መጀመር ጠቃሚ ቢሆንም ጽሑፌን ወደ መጽሐፍ ምእራፍነት እንዳይቀይረው በመስጋት፣ ከዚያ በላይ ደግሞ አንባቢዎቼ ስለማንነት እና ስለፖለቲካው መሠረታዊ ጉዳዮች ያውቃሉ ከሚል እምነት ስለማንነት ወደመዘርዘር አልገባም። በምትኩ ለክርክሬ የሚሆኑኝን መነሻዎች ብቻ እጠቅሳለሁ። አምስት ጭብጦች ላስይዝ፤
Map ethiopia
1.1. አንድ ሰው ብዙ አይነት ማንነቶች ሊኖሩት ይችላሉ፤ ይኖሩታልም። አንድ ማንነት በጉልህ የሚታየው ከሌላው ጋራ ሲነጻጸር እንደመሆኑ መጠን፣ አንድ ሰው ማንነቱን የሚገልጽበት መንገድ እንደሁኔታው ይለያያል። ጥያቄው ሃይማኖትን ሲከተል፣ ሃይማኖታዊ ማንነቱን ያስቀድማል እንደማለት። እዚህ የምናነሰው ግን ቋንቋን ጨምሮ ከተመሳሳይ ባህል፣ ታሪክ እና ስነልቦና ጋራ ስለተቆራኘው ማንነት ነው። የማንነት ፖለቲካ በአገራችን በዋናነት የሚወከለውም በዚሁ ነው። ለውይይታችን እንዲረዳ በብሔረሰባዊ እና በአገራዊ ማንነት ላይ ብቻ እናተኩር።

1.2.ማንነት (ብሔረሰባዊም ይሁን አገራዊ) ማኅበረሰብ ሠራሽ ነው፤ ተፈጥሯዊ አይደለም። ማንነት ከቤተሰብ፣ ከማኅበረሰብና ከትምህርት ቤት የምንማረው ነው። ስለዚህም ባለበት አይረጋም፤ መጠነኑና ፍጥነቱ ቢለያየም ይለወጣል።

1.3.ማንነት በአጋጣሚ በአንድ ማኅበረሰብ ውስጥ በመወለድ እና/ወይም በማደግ፣ አለዚያም በተጽእኖ ሊገኝ ወይም ሊለወጥ ይችላል። ይህ ብቻ ግን አይደለም። ማንነት በምርጫም ሊገኝ ይችላል፤ አንድ ሰው በፍላጎቱ የአንድ ማንነት አካል ሊሆን ይችላል፤ ምን ያህል ይሳካለታል የሚለውን የሚወስኑ ብዙ ከእርሱ ውጭ የሆኑ ሁኔታዎች ቢኖሩም። አንዳንድ ማኅበረሰቦችና ማንነቶች ከሌላው የበለጠ አዲስ መጤን የመቀበልና የማዋሐድ ጠባይ አላቸውና።

1.4. አንድ ማንነት ከቀላል ጀምሮ ወደ ውስብስብና ብዙ እንደሚያድግ ሁሉ፣ ማንነቶች ሊወራረሱ፣ አልፎም ማንነቶች ተደባልቀው/ተዋሕደው ”አዲስ/የተለየ” ማንነት ሊፈጥሩም ይችላሉ።
1.5. በማንኛውም መንገድ መስተጋብር የመፍጠር እድል ያገኙ ማንነቶች የተለያዩ እሴቶቻቸውን ይለዋወጣሉ፣ ይዋዋሳሉ፣ ያዳቅላሉ። እንዳለ የሚያስጠብቁት የማንነታቸው አካል መኖሩ እንደማይቀርም እሙን ነው። ስለዚህም ንጹህ የሚባል ማንነት አይኖርም። ንጹሕ የሚባል ማንነት ካለ ያ ማንነት በላቦራቶር የተፈጠረና እስካሁንም ወደምንኖርባት የሰው ዓለም ያልመጣ ማንነት ነው።

ከዚህ የሚከተለው ክርክሬ ቢያንስ በእነዚህ አምስት መንደርደሪያዎች ላይ የተመሠረተ ይሆናል። እነዚህን መነሻዎች ይዘን ወደ ጥያቄው እንመለስ። እውነት ኢትዮጵያዊ ማንነት የለም?

በአገራችን የብሔረሰብ ማንነት አለ፤ ራሱን የዚህ ወይም የዚያኛው ብሔረሰብ አባል አድርጎ የሚመለከት ሰውም አለ። ይሄ ለክርክር የሚቀርብ፣ ያልተረጋገጠ ጉዳይ አይደለም። ይህኛው ቡድን ”ብሔርሰብ ነው ወይስ ዘውጌ ወይስ ጎሳ?” የሚለው ጥያቄ ላነሳነው ክርክር አስፈላጊ አይደለም። ለአሁኑ፣ ቁም ነገሩ፣ የራሳችን ባህላዊና ታሪካዊ ማንነት አለን የሚሉና ያላቸው ብድኖች መኖራቸው ነው። ስለዚህ ”እኔ የእገሌ ብሔረሰብ አባል ነኝ፤ የዚያኛው አይደለሁም፤ ማንነቴም አገው፣ ትግራዋይ፣ ጉሙዝ፣ ኦሮሞ፣ አማራ…ነው” የሚሉ ሰዎች አሉ። መኖራቸው እውነት ነው፤ በአግባቡ ከተያዘም ጸጋ ነው። አሁን የቀረበው ጥያቄ፣ ኢትዮጵያ ውስጥ ያሉት እነዚህ ብሔረሰባዊ ማንነቶች ብቻ ናቸውን የሚል ነው። ወይም፣ ኢትዮጵያዊ ማንነት የለምን? እርግጥ የአንድ ማንነት ታጋሪዎች ነን የሚሉ ሰዎች እስካሉ ድረስ ስለማንነቱ ለማረጋገጥ ሌላ ምርመራ ማድረግ የግድ አይደለም ብሎ የሚከራከር ይኖር ይሆናል። በዚህ ስሌት፣ ”ኢትዮጵያዊ ማንነት አለን” የሚሉ ሰዎች መኖራቸው ብቻውን በቂ ማስረጃ በሆነ ነበር። ቢሆንም ተጨማሪ ሐሳቦችን መለዋወጡ አይጎዳም።

2. ኢትዮጵያዊ/አገራዊ ማንነት የለም የሚሉ ሰዎች ቢያንስ አራት ስሕቶችን ይፈጽማሉ።

2.1. ከፍ ሲል የጠቀስኩትን የማንነቶችን መወራረስ፣ አልፎም የአዲስ ማንነቶች መፈጠር አይቀበሉም። ይህ ማለት በኢትዮጵያ ውስጥ የሚገኙት ብሔረሰቦች (የፖለቲካ ማኅበረሰቡ አባል የሆኑት ወደውም ይሁን ተገደው) በታሪክ ባካሔዱት መስተጋብር የሁሉም ”ቅልቅል” የሆነ (ምናልባትም የሆኑ) አዲስ ማንነቶች ሊፈጠሩ እንደሚችሉ አይቀበሉም ማለት ነው። አዳዲስ ማንነቶች ሊፈጠሩ ይችላሉ ብለው ካመኑ ክርክራችን በአገራችን አዲስ ማንነቶች ስለመፈጠራቸው እና ስለተፈጠረው/ስለተፈጠሩት አዲስ ማንነቶች ስያሜ ይሆናል ማለት ነው። በእኔ እምነት፣ በረጅሙና በውስብስቡ የአገረ ኢትዮጵያ መስተጋብር አዳዲስ ማንነቶች ተፈጥረዋል። (ይህ ማለት የብሔረሰብ ማንነቶች ጠፍተዋል ማለት አይደለም፤ እርግጥ ባሉበት አንዳችም ሳይለወጡ ቀጥለዋል – ንጽሕ የሚለው ቁልምጫ ትርጉሙ እርሱ ይመስላል- ማለትም ቢያንስ ፖለቲካዊ የዋህነት ይሆናል።) ከተፈጠሩት ”አዲስ/የተለዩ” ማንነቶች አንዱና ዋናው ብዙዎቻችን ”ኢትዮጵዊነት” የምንለው ማንነት ነው። ስለዚህ ማንነት አይነቶች ወይም አረዳዶች ወደ ኋላ አነሳለሁ፤ የችግሩ መነሻ ”ኢትዮጵያዊነት” የሚለው ስያሜ ለተለያዩ ሰዎች የተለያየ ትርጉም መስጠቱ ሊሆን ይችላልና።

2.2. ተከታዩ ስህተት አንድ ሰው ከአንድ በላይ ማንነት ሊኖረው አይችልም፣ አንዱን ማንነት ሲቀበል ሌላውን መተው አለበት፣ ወይም የቀደመ ማንነቱን ከአዲስ ማንነት ጋራ ማዳበል ወይም ማዋሐድ አይችልም ከሚል የተሳሳተ አመለካከት የሚመነጭ ነው። ይህ በንድፈ ሐሳብም ሆነ በተግባር የተሳሳተ ነው። አሁን ያለችውን ኢትዮጵያ ተጨባጭ እውነታም መረዳት ይጎድለዋል። ዛሬ፣ ራሳቸውን በብሔረሰባዊም በአገራዊ ማንነታቸውም የሚገልጹ በሚልዮን የሚቆጠሩ ኢትዮጵያዊ ዜግነት ያላቸው ሰዎች አሉ። ልብ በሉ፣ ለእነዚህ ሰዎች ኢትጵያዊነት ዜግነት ብቻ አይደለም፣ ማንነትም ጭምር ነው። ራስን በብሔረሰብ ማንነት ብቻ ሳይሆን በሃይማኖት ማንነትም ደርቦ መግልጽ እንደሚቻለው፣ ኢትዮጵያዊነትን ተጨማሪ ማንነት ማድረግ እውነት የማይሆንበት ምክንያት አይታየኝም። ብሔረሰባዊም አገራዊም ማንነት ያለቸው ሰዎች ስለመኖራቸው ማረጋገጥ ከባድ አልመሰለኝም። አገራዊ ማንነት የለንም የሚሉ ሰዎችን የግድ ይኑራችሁ ብዬ አልከራከርም። ዝርዝሩ ሌላ ውይይት ይፈልጋልና ልተወው።

2.3. ኢትዮጵያዊ ማንነት የለም የሚሉት ሰዎች የሚሰሩት ሌላው ስሕተት ከፍትሕ ጋራ የተያያዘ ነው። እነርሱ ታሪካዊቷ ኢትዮጵያ ”ማንነታችንን ሳታከብር ኖራለች፣ እውቅና ተነፍገን ኖረናል፣ ይህም ሊለወጥ ይገባል” ብለው ይከራከራሉ። ተገቢና እውነት ያለው የፍትሕ ጥያቄ ነውና ከልቤ እደግፈዋለሁ። ይህን እነርሱ የሚጠይቁትን ፍትሕ ግን ለሌሎች፣ ዛሬ ኢትዮጵያዊ የሚባል ማንነት አለን ለሚሉትን ወገኖቻቸው እየከለከሉ ነው። አሁንም ስለዚህ ኢትዮጵያዊ ማንነት ወደ ኋላ አነሳለሁ።

2.4. እነዚህ ሰዎች ከሚሰጡት ማብራሪያ የምንረዳው ሌላው ጭብጥ እውነተኛው/ደንበኛው ማንነት በብሔረሰብ ላይ የተመሰረተው ነው የሚል ነው። እነርሱ ባወጡት የማንነቶች ደረጃ መሠረት፣ ከብሔረሰባዊ ማንነት ውጭ ያሉት ማንነቶች አንድም ውሸት ናቸው አለዚያም ጠንካራ አይደሉም። ብሔረሳባዊ ማንነት ከሌሎቹ ማንነቶች ቀዳሚነት እንዳለው ይሰብካሉ። ይህንን ለፖለቲካ መቀስቀሻነት የሚጠቀሙት ሰዎች ዓላማ የተሰወረ አይደለም። ሐሳቡ ግን በግማሽ እውነት ላይ የተመሰረተ ስንኩል መከራከሪያ ነው። ግለሰቦችና ቡድኖች የሚያስቀድሙት የማንነት መለያ የሚወሰነው በኖሩበትና ባሉበት ታሪካዊ ሁኔታ እንጂ አስቀድሞ በወጣ የማንነቶች ደረጃ አይደለም። ከሌላው ማንነቱ በፊት በሃይማኖታዊ ማንነቱ ራሱን የሚገልጽ ሰው/ቡድን ይኖራል፤ ለሌላው ደግሞ ብሔረሰባዊ አለዚያም አገራዊ ማንነቱን ቀድሞ ይሰማው ይሆናል። ሁሉም የማኀበረሰባቸው ታሪክ ውጤቶች ናቸው። አንዱ ከሌላው የበለጠ ትክክል አይደለም፤ እንደ ግለሰቡ እና ቡድኑ ሊለያይና ሊለዋወጥ የሚችልም ነው። ይህ አመለካከት አንዳንድ ጊዜ ብሔረሰባዊ ማንነታቸውን የማያስቀድሙ ሰዎችን ”የማንነት ችግር” እንዳለባቸው ወይም እየዋሹ እንደሆነ የመክሰስ ድፍረት ተላብሶ የሚታይበት ጊዜም አለ።

3. ኢትዮጵያዊነቶች?

እንደማንኛውም ማንነት ኢትዮጵያዊነትም ብዙ ገጽታዎች አሉት። በታራካዊ ሂደቶችም ብዙ ተለውጧል፤ ገና ይለወጣልም። ኢትዮጵያዊ ማንነት ብዙ ገጽታዎች አሉት ወይም ብዙ አይነት ኢትዮጵያዊ ማንነቶች አሉ ብሎ መነሳት ይቻላል። ለዚህ ጽሑፍ አግባብነት አላቸው ያልኳቸውን ሦስት የኢትዮጵያዊ ማንነት አረዳዶች ብቻ ላስቀምጥ።፡ይህን የማደርገው፣ ኢትዮጵያዊ የምንለው ማንነት ለተለያዩ ሰዎች የተለያየ ትርጉም እየሰጠ አለመግባባት ፈርሮ እንደሆነ በሚል መነሻ ነው። ለመግባባት ሲባል ለማንነቶቹ ሌላ ስያሜም መስጠት እንችል ነበር፣ ለጊዜው ይቆየን።

3.1. አንደኛው ኢትዮጵያዊ ማንነት ራሱን የሁሉም የአገራችን ብሔረሰቦች አካል አድርጎ ይመለከታል፤ ለአንዱ የተለየ ቅርበት አይሰማውም። እነዚህ ሰዎች ምክንያቱ ምንም ይሁን፣ ራሳቸውን የዚህ ወይም የዚያኛው አንድ ብሔረሰብ አባል አድርገው አይቆጥሩም። የዚህ ማንነት ባለቤት የሆነው ኢትዮጵያዊ፣ በአገሪቱ ውስጥ የሚገኝ ማንኛውም ነገር እኩል ተጋሪ ባለቤት እንደሆነ ያምናል። ብሔረሰባዊ ማንነትን ያከብራል። ብሔረሰባዊ ማንነትን ተገዳዳሪው አድርጎ አይፈራውም። ይህ ማንነት ድንገት ከሰማይ ወርዶ የሁሉም አካል ነኝ የሚል፣ ባለቤት አልባ ማንነት አይደለም። በአብዛኛው በተለይ በከተሞች አካባቢ ያደጉ (ለረጅም ጊዜ የኖሩ) ሰዎች የዚህ ማንነት ተጋሪዎች ናቸው። ባህላዊና ስነልቦናዊ ማንነታቸውን የቀረጸው ያለፉበት ታሪክ ነው፤ ፖለቲካው፣ ጦርነቱ፣ የሕዝብ እንቅስቃሴውና መስተጋብሩ፣ ትምህርቱ፣ የከተሜ ኑሮ…። ለእነዚህ ሰዎች ኢትዮጵያዊነት ዜግነት ብቻ ሳይሆን ማንነትም ጭምር ነው። ቁጥር የበለጠ ትርጉም የሚሰጣቸው ሰዎች ካሉ፣ የዚህ ማንነት ባለቤቶች ቢያንስ በሚልዮኖች የሚቆጠሩ ስለመሆናቸው አልጠራጠርም። (እኔም ራሴን ያገኘሁት እና መሆንም የመረጥኩት እዚህ ውስጥ ነው።)

3.2. ሁለተኛው ኢትዮጵዊነት የአንድ ብሔረሰብ ማንነት ያለው፣ ነገር ግን በተጨማሪም ኢትዮጵያዊ ማንነት ያለው ነው። በብሔረሰብ ማንነቱ የብሔረሰቡ የሆነውን ሁሉ ይጋራል፤ እዚያ ግን አያቆምም፤ በኢትዮጵያዊ ማንነቱ ከሎሎች ኢትዮጵያዊ ማንነት ካላቸው ጋራ የሚጋራው ሌላም ብዙ ነገር አለ። ይህ ሰው የሚረዳው ኢትዮጵያዊ ማንነቱ፣ ብሔረሰባዊ ማንነቱን እንዲተው የሚጠይቅ አይደለም። ይህ ማንነት፣ ከከተሞች መስፋፋት፣ ከትምህርትና ከመንግሥት ቢሮክራሲ ዝርጋታ ጋራ እያደገ እንደመጣ እገምታለሁ። አሁንም የዚህ ቡድን አባላት ቁጥር ከአገሪቱ ሕዝብ ከግማሽ በላይ እንደሚሆን አልጠረጥርም። ይህ ባይሆን አገሪቱ ህልውናዋ ባከተመ ነበር ከሚል መነሻ።

3.3. ሦስተኛው ኢትዮጵያዊነት፣ ብሔረሰባዊ ማንነትን የሚክድ ወይም ለማጥፋት የሚፈልግ ተጻራሪ ማንነት አድርጎ የሚመለከት አረዳድ ነው። ከታሪክ አንጻር በከፊል እውነት ነው። ለዚህ አረዳድ፣ ኢትዮጵያዊነት ማለት የክርስቲያን ሰሜን ኢትዮጵያ ባህልና ማንነት ነው። እንደ ጉዳዩ አቅራቢ ይህ ኢትዮጵያዊነት የአማራ ባህልና ማንነት ብቻ ተደርጎ የሚቀርብበት አጋጣሚም አይጠፋም። ለዚህ አመለካከት አስፈላጊው ጭብጥ ግን፣ ”ኢትዮጵያዊ” ማንነት ቀድሞም ይሁን አሁን ሌሎች ባህላዊ ማንነቶችን ለመደፍጠጥ ያሰፈሰፈ ማንነት ተደርጎ መታየቱ ነው። ይህ መሠረተ ቢስ ስጋት ነው ብዬ እንዳልደመድም እነርሱ ”ኢትዮጵያዊነት” ከሚሉት ውጭ ያለ አገራዊም ሆነ ብሔረሰባዊ ማንነት እንዲጠፋ አዋጅ ማወጅ የሚቃጣቸው ሰዎች አሉ። ማለት የምችለው፣ የእኔ ኢትዮጵያዊነት ከዚህ ይለያል። ይህ የኢትዮጵያዊ ማንነት አረዳድ የብሔረሰብ ማንነቶችን የማያከብር፣ ስለመኖራቸውም ሙሉ እውቅና የማይሰጥ ነው። ይህ ኢትዮጵያዊነት ብሔረሳባዊ ማንነቶችን በጥርጣሬ ይመለከታል፣ የአገራዊ መተሳሰር ጠላቶች አድርጎ ይፈርጃል፣ ማንነቶቹን ማዳከምም ይፈልጋል። የዚህ ማንነት አቀንቃኞች በአብዛኛው በአማራ ልሒቃን መካከል የሚገኙ ጥቂቶች ናቸው። እንዳለመታደል ሆኖ ኢትዮጵያዊ ማንነት በዚህ ገጽታው ብቻ ሲወከል ይስተዋላል።

ህወሓት/ኢሕአዴግ በስልጣን ዘመኑ የመጀመሪያ አስር ዓመታት ሆን ብሎ ሁሉንም ኢትዮጵያዊነቶች በጅምላ እንዲጠሉ ብዙ ሰርቷል። ሌሎቹ ብሔረሰብ ተኮር ፓርቲዎችም ከሞላ ጎደል ተመሳሳይ ስትራቴጂ ተከትለዋል። ስጋታቸው ግልጽ ነው፤ የብሔረሰባቸው አባላት ኢትዮጵያዊ ማንነትን ከደረቡ የደጋፊ መጠናቸው ሊቀንስ ይችላል። በውጤቱም፣ ዛሬ፣ ”ኢትዮጵያዊ ማንነት” ሲባል በብዙ የአደባባይ ሰዎች ዘንድ አስቀድሞ የሚጠቀሰው ይህ ሦስተኛው አመለካከት ብቻ ሆኗል። የፖለቲካ ልሒቃኑ ኢትዮጵያዊነትን በቀዳሚዎቹ ሁለት መልኮቹ የሌለ በማስመሰልም፣ ሦስተኛውን ግን በማጉላት፣ የማንነቱን ባለቤቶች በጅምላ ጥፋተኞችና ተጠርጣሪዎች አስመስለው ያቀርቧቸዋል። ይህ ስህተት ብቻ ሳይሆን ሸፍጥም ነው። የሸፍጥነቱ ስላቅ ወደዜኒቱ የደረሰው፣ እነመለስ ደርሶ የሁለተኛው ዓይነት/አረዳድ ኢትዮጵያዊነት (3.2) አራማጆች ሆነው፣ ባንዲራ መስቀልና ስለሺህ ዓመት የኢትዮጵያ ታሪክ መስበክ ሲጀምሩ ነበር። ሌላው በጣም የሚገርመኝ ነገር፣ የመጀመሪያው ዓይነት ኢትዮጵያዊ ማንነት ያላቸው ዜጎች መኖራቸውን ገዢው ፓርቲ ጭምር ዛሬም ድረስ እውቅና ለመስጠት መፍራታቸው ነው።

ብሔረሰባዊ ማንነትን የፖለቲካቸው ማቀጣጠያ አድርገው መጠቀም የሚፈልጉ ልሒቃን፣ እንዲሁም ከማንነት ፖለቲካና የውድድር ስሜት የሚመጣው ስሜተ-ስሱነት የሚያስከትለውን ሚዛን የመሳት አደጋ ቀድመው ያልጠረጠሩ ሰዎች፣ በአገራችን ውስጥ ያሉት ብሔረሰባዊ ማንነቶች ብቻ ናቸው ይላሉ። ይግረማችሁ በማለትም፣ ኢትዮጵያዊ ማንነት የለም ይላሉ።

ማንኛውም ማንነት እና ከእርሱ ጋራ ተያይዘው የሚመጡ ስሜቶች (የኩራት-ሃፍረት፣ የበላይ-የበታችነት፣ የአሸናፊ-ተሸናፊነት፣ የጊዜው የእኛ ነው-አይደለም፣ የተስፋ-ስጋት ወዘተ) መኖራቸውን ማስቀረት ባይቻልም መጠናቸውን ሲያልፉ ከፍተኛ አደጋን ይጋብዛሉ። አደጋው ሐልዮታዊ ብቻ ሳይሆን ማኅበረሰባዊም ነው። በሐልዮት ደረጃ፣ አሁን እንደምናየው፣ ”ያለሁት እኔ ነኝ እንጂ አንተ አይደለም” እስካማስባል ያደርሳል። አገራችንም ሆነች ዓለማችን በዚህ መሰሉ ሚዛኑን የሳተ የማንነት ስሜት ብዙ ዋጋ ስለመክፈላቸው ታሪክ ብዙ ያስነብበናል። አገራዊ ማንነት ሲጦዝ ሌላውን አገር በእብሪት ወደ መውረር ስካር ያመራል፤ በቆዳ ቀለም መኩራት (የሚያኮራ ከሆነ) ከዚያ አልፎ የበላይነት ማረጋገጫ ሰርተፊኬት ሆኖ ሲወሰድ ወደ አፓርታይድ ያደርሳል፤ በብሔረሰባዊ ማንነት ኮርቶ ራስን ማስተዳደርና ባህልን ማዳበር ከዚያ አልፎ የሌላውን (በተለይ ተፎካካሪ ተደርጎ የሚቆጠረውን) ማንነት መኖርና አለመኖር (በሐልዮትም ይሁን በአካል) ለመወሰን ወደሚያስችል ስልጣንነት ሲቀየር የመጠፋፋት በር ማንኳኳቱን ልብ እላለሁ፤ እሰጋለሁም።

ማንኛውም ብሔረተኝነት በጋራ ታሪክና መጻኢ እጣ ሚዛን መገደብ አለበት። ይህ ካልሆነ፣ ገደብ አልባ በራስ የመተማመን እና የእርግጠኝነት ስሜት ይፈጥራል። ትህትናንና መተሳሰብን ከግለሰብ ልብ፣ ከቡድን የጋራ ስነልቦና ያጠፋል። ይህ ስሜት በግለሰብም በቡድንም ደረጃ ሊንጸባረቅ ይችላል።

ኢትዮጵያዊ ማንነት አለ። ኢትዮጵያዊ ማንነት የሚለው አገላለጽ የሚወክለው መጥፎ የታሪክ አሻራም አለ። የመጥፎው አሻራ ባለቤት የሆነው የኢትዮጵያዊነት አረዳድ በሒደት እየተዳከመ መሔዱ ግልጽ ነው። ምኞቴም ነው። ሌሎቹ ሁለቱ አይነት ኢትዮጵያዊ ማንነቶች ግን የታሪካችን ተጨባጭና በጎ ውጤቶች አድርጌ አያቸዋለሁ። ምንልባትም መጻኢው የኢትዮጵያ መልካም እጣም ያለእነርሱ እውን የሚሆን አይመስለኝም። ራሴንና መሰሎቼን እንዴት ከነገው መልካም ቀን አውጤቼ ልመለከት እችላለሁ? እንዴትስ፣ ”እንኳን የነገው አካል ልትሆን፣ ዛሬም የለህም” ስባልስ ዝም እላለሁ?! ኢትዮጵያዊነት አለ። የለም ስለተባለም አይጠፋም። እኔ አለሁ።

* መስፍን ይህ ጽሁፍ በፌስቡክ ሰሌዳው ላይ ያቀረበው ነው። ጽሁፉን በፌስቡ ለማየት እዚህ ይጫኑ

ሕወሓት ከመለስ ጋር አብሮ ተቀብሯል –ክፍል 2

$
0
0

Bereket Simon weeping with his wife over Meles Zenawi's death
ከነፃነት አድማሱ
dalul@gmail.com

የሰው ልጅን ነፃነት የማይገባው ነፃ አውጪ!!

በትግራይ የህወሓት እኩይ ተግባር በቅርብ የተከታተሉት አንድ የሽሬ እንዳስላሴ አዛውንት እንዲህ በማለት በምሬት ይገልፁታል። “ደርግ ሰው ገድሎ በአደባባይ ይፎክር ነበር። ዛሬ ህወሓት ግን ሰው ገድሎ ልቅሶ ይደርሳል” ሲሉ የድርጅቱን እርኩስነት፣ አስከፊነትና የሰብኣዊ ፍጡር ባላንጣነት ካለፈው የደርግ አገዛዝ ጋር በማነፃፀር ቁጭታቸውን በትካዜ ሲናገሩ አጋጥሞኛል። የዛሬው ፅሑፌም ካለፈው ክፍል አንድ የቀጠለ ነው። በክፍል አንድ የተነሱ ዋና ዋና ጥያቄዎችም በኋላ በዝርዝር ለማስቀመጥ እሞክራለሁ። ለዛሬ ግን ቀደም ብዬ በክፍል አንድ የጀመርኩትን “አደናግረህ፣ አስፈራርተህ፣ አሸብረህ፣ ወገን ከወገኑ ጋር አናቁረህና ለያይተህ ግዛ” የሚለውን የህወሓት የደደቢት የደንቆሮ ፍልስፍናና መፈክር በሚመለከት አጭር ማጠቃሊያ በማከል ፅሑፌን እቋጫለሁ።

ሙሉውን ለማንበብ እዚህ ይጫኑ

አሜሪካውያን ባለስልጣኖችን ያጃጃለ አለማቀፍ አራዳ፤ በብርሃኑ አስረስ መጽሐፍ መነሻነት

$
0
0

ከክፍሉ ሁሴን

penራሱን ካልናቀ እና ጣል ጣል ካላደረገ በቀር ማንኛውም ጎልማሳ የተካበተ፣ሊወሳ እና በታሪክ ሊዘከር የሚችል የሕይወት ልምድ አለው።አንዳንዶች እንዲያውም የራሳቸውን ግለ ሕይወት ብቻ ሳይሆን ጠቅላላ የአንድን ማህበረሰብ ታሪክ በእጅጉ ሊመለከት ከሚችል ሁነት ጋር ባጋጣሚ ይገናኙና የታሪክ ሁነቱ አካል ወይም ማዕከል እስከመሆን ይደርሳሉ።የሚያሳዝነው በኛይቱ አገር ይህንን አውቀን ማስታወሻ በመያዝ ለሚቀጥለው ትውልድ ትምህርት እንዲሆን ትውስታችንን በጽሁፍ የምናበረክት እጅግ ጥቂቶች ነን።ለዚህም ነው በቅርቡ ያነበብኩትን የ “ማን ይናገር የነበረ–የታኅሣሡ ግርግር እና መዘዙ”ን መጽሐፍ ደራሲ አቶ ብርሃኑ አስረስን ለማድነቅ፤ከማድነቅም አልፎ በመጽሐፋቸው የተነሱት አንዳንድ የታሪክ ሁነቶች እኔንም በትውስታ ብልጭታ (flashback )ወደኋላ ስለወሰዱኝ ይህንኑ በማነሳሳት ሌሎች ልክ እንደ አቶ ብርሃኑ አስረስ የተካበተ ልምድ ያላቸው እንዲሁም አገራችንን በሚመለከት የታሪክ ሁነት በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ የተሳተፉ እንዲጽፉ ለመጎንተልም ጭምር ነው።እርግጥ ባሁኑ ወቅት የግለ ሕይወት ታሪክ (Autobiography )መጽሐፍ ትንሳኤ የሆነ እስኪመስል ድረስ ታዋቂም፤ እጅግም ታዋቂ ያልሆኑ ግን ባንድ የታሪክ ክስተት የተሳተፉ ሰዎች የጻፏቸው መጽሐፍት በብዛት እየታተሙልን በማንበብ ላይ እንገኛለን።በዚህ አይነት በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ (አአዩ) ፕሬስ ከታተሙት መጽሓፍት ይህን እንድጭር የጎነተለኝ የአቶ ብርሃኑ መጽሐፍ አንዱ ነውና ዩኒቨርሲቲውንም በዚህ አጋጣሚ ይበል ይበል ማለት ተገቢ ይመስለኛል።

ሙሉውን ለማንበብ እዚህ ይጫኑ/PDF

Health: የጨጓራ ህመሜ ወደ ካንሰርነት ተቀይሮ ይሆን? መፍትሄውን ጠቁሙኝ እባካችሁ

$
0
0

ዕድሜዬ 43፣ ፆታዬ ወንድ፣ ስራዬ ደግሞ በግል ስራ የምትዳደር፣ ባለትዳርና የሁለት ልጆች አባት ነኝ፡፡ ከልጅነቴ ጀምሮ የተጠናወተኝ ጨጓራ እስካሁን ያሰቃየኛል፡፡ አንቲ አሲድ ሽሮፕና የጨጓራ ክኒኖች ቀለቦቼ ናቸው፡፡ በሳምንት ውስጥ ውስጤ ሳይቃጠል በሰላም የማሳልፋቸው ቀናት ሁለት አይሞሉም፡፡ የጭንቀቴ መንስኤ ግን ይህ የጨጓራ ህመም ብቻ እንዳይመስላችሁ፡፡ እንደ እኔው በኃይለኛ ጨጓራ ሲቸገር የነበረው አባቴም በመጨረሻ ችግሩ የጨጓራ ካንሰር ሆኖ ተገኘ፡፡ ሐኪሞቹም በኦፕሬሽን ሊሞከር ከሚቻለው በላይ ተስፋፍቷልና ጨረር ይሞከርለት ተብሎ ነበር፡፡ እሱም ብዙም ሳይረዳው ካረፈ ዓመት ሞላው፡፡ እናም እኔም ጨጓራዬ በለበለበኝ፣ ቃር በበዛብን ቁጥር ውስጤን ከሚሰማኝ የማቃጠል ፀባይ ይበልጥ የሚረብሸኝ ወደ ካንሰርነት ተቀይሮ ይሆን? ወይ የሚለው ስጋቴ ነው፡፡ ይሄን ስጋቴን በምን ላጥፋው? ወደ ካንሰርነት ተቀይሮ ከሆነስ የኦፕሬሽ ጥቅም እምን ድረስ ነው?
ተድላ ነኝ

ask your doctorየዶ/ር ዓብይ ምላሽ፦ ውድ ተድላ ጥያቄህን ከአክብሮት ጋር በሚከተለው መንገድ አስተናግደነዋል፡፡ በተለምዶ ጨጓራ እያልን የምንጠራው ህመም ለጨጓራ ብቻ የተወሰነ ህመም ሳይሆን ትንሹን አንጀት ጨምሮ በተናጠል ወይንም በጋራ የውስጥ ግድግዳቸው ተልጦ ሲቆስል የሚኖር የማቃጠል የህመም ስሜት ነው፡፡ ቃር፣ ደረት እና ከእምብርት በላይ ማቃጠል፣ ጀርባ እና ውስጥ እጅ መንደድ፣ ማግሳት፣ ማቅለሽለሽና ማስመለስ ሁሉ ከጨጓራ ህመም ምልክቶች ሊመደቡ ይችላሉ፡፡ የጨጓራ ካንሰርም ተመሳሳይ ምልክቶች ሊኖሩት ሲችሉ ጨጓራ ካንሰር ቁስሉ የሚገኘው ግን እዛው ጨጓራ ውስጥ ብቻ ነው፡፡ የካንሰርነት ባህሪይ ያላቸው ሴሎች ግን ከጨጓራም አልፈው አካባቢውን ሊያዳርሱት ወይንም በደም እና ሊምፍ አማካኝነት ወደ ሩቅ ቦታ ሊዛመቱ ይችላሉ፡፡

ውድ ዓለሙ አባትህን በጨጓራ ካንሰር ማጣትህ ጭንቀትህን ቢያንረው አያስገርምም፡፡ አስፈላጊውን ምርመራዎች በማድረግ ግን ይህን ጭንቀትህን ማስወገድ ትችል እንደነበር ስንነግርህ አሁንም አልረፈደምና ምርመራዎችን ልታደርጋቸው እንደምትችል ልናሳስብህ እንወዳለን፡፡

በመጀመሪያ የጨጓራ ካንሰር ጠቋሚ ምልክቶችን ለማብራራት ያህል የሚከተሉትን ነጥቦች ልብ በል፡፡ የጨጓራ ካንሰር ዕድሜ ሲገፋ ይበልጥ የሚስተዋል ህመም እንደመሆኑ
ከአርባ ዓመት ዕድሜ በኋላ ድንገት የሚጀምር የጨጓራ ህመምን በቸልታ ማለፍ አያስፈልግም፡፡ አዲስ የተነሳ የጨጓራ ህመም ብቻም ሳይሆን ድንገት ከአርባዎቹ ዕድሜ በኋላ ተባብሶ እረፍት የሚነሳ የጨጓራ ህመምንም ሐኪም ጋር ቀርቦ የጨጓራ ካንሰር አለመሆኑን ማየት ያስፈልጋል፡፡

ክብደት መቀነስ፣ ሆድ ላይ የሚስተዋል እብጠት ወይንም ምግብ መዋጥ አለመቻልም እንዲሁ ከጨጓራ ህመም ምልክቶች ጋር በህብረት ከታዩ የጨጓራ ካንሰር ተከስቶ ሊሆን ይችላልና መዘግየት አያስፈልግም፡፡

ask your doctorከሁሉ ይበልጥ ግን የጨጓራ ክኒኖችን እየዋጥክ የማቃጠል ስሜቱን ለማሸነፍ ከመጣር ይልቅ በደንብ ልትመረመር እና ልትታከም ይገባል፡፡ በቀላሉ አልታገስ ያለ የጨጓራ ህመም ሔሊኮባክተር ፓይሎሪ በሚባለው ባክቴሪያ አማካኝነት የተነሳ የጨጓራ ህመም ሊሆን ይችላልና በቀላል የደም ምርመራ ማወቅ ይቻላል፡፡ ህክምናውም እጅግ ቀላል ሲሆን ሶስት አይነት መድሃኒቶችን (ሁለት አይነት አንቲ ባዮቲክስ እና አንድ የአሲድ ምርት የሚቀንስ ታብሌት) ለሁለት ሳምንት ብቻ በመውሰድ ለዓመታት የጨጓራ ህመም እንዳይመለስ ያደርጋል፡፡

ባክቴሪያው በደም ምርመራ እንደሌለ ከተረጋገጠና ሐኪምህ የጨጓራህን ቁስል ባህሪይ ለማወቅ ከፈለገ (የካንሰርነት ባህሪይ ይኑረው፣ አይኑረው) የራጅ ምርመራ ያደርግልሃል፡፡

ይሄኛው የራጅ ምርመራ ግን ከተለመደው የተለየ ነው የሚሆነው፡፡ ምክንያቱም የጨጓራህን ውስጣዊ ግድግዳ ያለበትን ሁኔታ በራጁ እንዲታይ አስቀድመህ የምትጠጣው ኬሚካል ይኖራል፡፡ ወይንም ደግሞ ሐኪምህ በኢንዶስኮፒ የጨጓራህን ውስጣዊ ግድግዳ ሊመለከትና ከተጠራጠረም ከቁስሉ አካባ ናሙናዎችን ወስዶ በፓቶሎጂ ምርመራ የካንሰርነት ባህሪይ እንዳለውና እንደሌለው ማረጋገጥ ይችላል፡፡

ገና በ43 ዓመት ዕድሜህ ህመምህ የጨጓራ ካንሰር የመሆን ዕድሉ እጅግ አናሳ ቢሆንም ጥያቄህን ለመመለስ ያህል ለጨጓራ ካንሰር የሚደረገው ህክምና በዋነኝነት በኦፕሬሽን ቆርጦ ማውጣት መሆኑን ልንጠቁምህ እንወዳለን፡፡ በሽታው ሳይሰራጭ ከተደረሰበት ከካንሰሩ ሙሉ ለሙሉ የመፈወስ እድል ሲኖር ብዙው ጊዜ ግን ይህ አያጋጥምህም፡፡ በተጨማሪም ከቦታው አልፎ ለተስፋፋ የጨጓራ ካንሰር ከኦፕሬሽ ጎን ለጎን የጨረር ህክምና መስጠትም ይቻላል እያልን ወድ ተድላ ሳትዘገይ ሐኪም ዘንድ ቀርበህ ትታይ ዘንድ በድጋሚ እንመክርሃለን፡፡

ምኒልክን ብትወቅሱ ማንነታችሁን ትረሱ –ከኃይሌ ላሬቦ (ባለ 51 ገጽ ሰፊ ትንታኔ)

$
0
0

minilik
የኔልሶን ማንደላን ለቅሶና ቀብር ሳይ በጣም ተገረምሁ ብቻ ሳይሆን እፍሪቃዊ መሆኑ ራሱ አኰራኝ። ከዚህም ተነሥቼ፣ታሪክን ወደኋላ መለስ ብዬ በኅሊናዬ መስተዋት ቃኝቼ ሳበቃ፣ ጊዜው እንደዛሬ ሁኖ ቢያመችለት ኖሮ፣ እንደሳቸው ሊለቀስ የሚገባ ሰው በአፍሪቃ ምድር ከዚህ በፊት ታይቶ አይታወቅምን ብዬ ራሴን በራሴ ደጋግሜ ጠየቅሁ። ማንዴላ የሚደነቁት፣ በቀለሙ በመጀነንና፥ በዘመናዊ መሣርያው በመተማመን፣ በበላይነት ረግጬው ልግዛው ብሎ፣ ለብዙ ዘመናት በሥልጣን ላይ ሁኖ ያሠቃይ የነበረውን ጨቋኙን የነጮች ግዛት ከነሥርዐቱ አሸንፈው፣ ለሀገራቸው ጥቊር ሕዝብ የድል ዋንጫ አጐናፅፈው፣ ነፃነቱንና ክብሩን ስለመለሱለት ነው። ግፈኞቹን የድሮ ጠላቶቻቸውንም እንደመበቀል ፈንታ በፍቅር ያዟቸው። ሁሉም የደቡብ አፍሪቃ ዜጋ በጐሣና በዘር፤ በሃይማኖትና በቀለም ሳይለያይና ሳይከፋፈል፣ ታዲያ በመቻቻል፣ ባንድነትና በፍቅር ተቀራርቦ እንዳንድ ሀገር ሕዝብ እንዲኖር አደረጉ። ለኻያ ሰባት ዓመታት በእስራት ራሳቸውን በመሠዋት፣ ጠላታቸውን በማሸነፍ፣ ራሳቸውንና ሀገራቸውን ያኰሩ ደግና ብልህ መሪ፣ ሰውን በማንነቱና በእምነቱ ሳይሆን በሙያውና በችሎታው የሚፈርጁ፤ ጠላትን እንኳ የሚራሩና የሚወዱ ሰው ነበሩ። ይኸንን በዐይነ ኅሊናዬ መላልሼ ካሰላሰልሁ በኋላ፣ የዓለምን ታሪክ ደግሞ ቃኝቼ ሳበቃ አንድ እጅግ በጣም ታላቅ ሰው አገኘሁ። አፄ ምኒልክ።

ሙሉውን ለማንበብ እዚህ ይጫኑ/PDF

ሕንድ ወደ ሃገሯ የሚገቡ ኢትዮጵያውያንን እና ወደ ኢትዮጵያ የሚጓዙ ዜጎቿን የፖሊዮ ክትባት እንዲወስዱ አዘዘች

$
0
0

polio
(ዘ-ሐበሻ) ሕንድ ወደ ሃገሯ የሚገቡ ኢትዮጵያውያን የፖሊዮ ክትባት እንዲወስዱ የሚያስገድድ ሕግ ማውጣቷ ተሰማ። ፖሊዮ ወይም የልጅነት ልምሻ በቫይረስ ምክንያት የሚነሳ በሽታ ሲሆን፣ አካልን ከማጉደል ባሻገር ህይወት እስከ ማሳጣት ያደርሳል። በሽታውም ቀጥታ የሚያድን መድኃኒትም የለውም።

ዘሒንዱ የተባለው የህንድ ጋዜጣ ዛሬ እንዳስነበበው ከመጪው ማርች 1 ቀን 2014 ዓ.ም ጀምሮ ኢትዮጵያን ጨምሮ ማንኛውም የፖሊዮ ተጠቂ የሆኑ ሃገራት ዜጎች ህንድ ከመግባታቸው በፊት የፖሊዮ ክትባት እንዲወስዱ አዲስ የወጣው ህግ ያስገድዳል።

የሕንድ ጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ከህንድ ወደ ፖሊዮ ተጠቂ የሆኑ ሃገራት ለሚጓዙ ዜጎቹም ለአንድ ዓመት የሚቆይ OPV የተባለ ክትባት (oral polio vaccine) ያዘጋጀ ሲሆን የአፍጋኒስታንን፣ የናይጄሪያን፣ የፓኪስታንን፣ የኢትዮጵያን፣ የኬንያን፣ የሶማሊያን እና የሶሪያን ሃገራት ከፖሊዮ ተጠቂ ሃገራት በመመደብ ወደነዚህ ሃገራት የሚጓዙ ዜጎችም ሆነ ወደ ህንድ የሚገቡ የነዚህ ሃገራት ዜጎች የፖሊዮ ክትባት እንዲወስዱ ከማርች 1 ቀን ጀምሮ ያስገድዳል።

እንደ ሚንስቴር መስሪያ ቤቱ ገለጻ የOPV ክትባት የወሰዱ ዜጎች ሰርተፊኬት የሚሰጣቸው ሲሆን ሰርተፍኬቱ ለአንድ ዓመት ያገለግላል። የOPV ክትባትን በየትኛውም ዕድሜ ክልል ያለ ኢትዮጵያን ጨምሮ ከላይ ከተጠቀሱት 7 ሃገራት የሚመጡ ዜጎችም ሆኑ ወደዚያ ሃገር የሚጓዙ የህንድ ዜጎች መውሰድ አለባቸው ሲል የሂንዱ ዘገባ ጨምሮ ገልጿል።

ኢትዮጵያ በ2008 ዓ.ም ፖሊዮን ከኢትዮጵያ አጥፍቻለሁ ስትል ብታውጅም ባለፈው ኦገስት ላይ ግን በምስራቁ የሃገሪቱ ክፍል የፖሊዮ ተጠቂ መገኘቱ አነጋጋሪ ሆኖ ቆይቷል። ባለሙያዎች እንደሚሉት በሶማሊያና በኬንያ እስካሁን ድረስ የፖሊዮ ቫይረስ ያልጠፋ በመሆኑ ወደ ምስራቁ የኢትዮጵያ ክፍል መግባቱ ብዙም ላያስገርም ይችላል ይላሉ።


የማለዳ ወግ …በጅዳ አለም የኢትዮጵያውያን አቀፍ ት/ቤት ከትምህርት ጥራት እስከ ባለሙያው ፈተና

$
0
0

ነብዩ ሲራክ ከሳዑዲ አረቢያ
Saudi arabia ethiopian school
ባሳለፍነው ሃሙስ የወላጅ መምህራን ስብሰባ ላይ ስለጅዳው አለም አቀፍ የኢትዮጵያውያን ትምህርት ቤት አስተዳደር ፍትሃዊነት የቅጥር ሂደት እና በትምህርት ጥራቱ ዙሪያ ላይ አንድ በኢኮኖሚክስ ትምህት በከፍተኛ ማዕረግ የተመረቀ ወጣት የሰላ ሂስ አቀረበ። በቀረበው የወጣቱ የዩኒቨርስቲ መምህር ስደተኛ ስራ ፈላጊ አስተያየት ድጋፍና ተቃውሞ ቤቱን በየተራ ናጠው ። በትምህት ጥራት አለመኖር የሚስማማው ወላጅ በጭብጨባ ድጋፉን ሲገልጽ የትምህርት ጥራቱን አንድ ከኢትዮጵያ ትምህርት ቤት የ12 ኛ ክፍል ተማሪ ጋር በእንግሊዝኛ ትምህርት እውቀታቸው የኤርትራ ኢንባሲ የ7ኛ ክፍል ተማሪ እንደሚልቅ በንጽጽር ማቅረቡ የተከፉ የህዝባዊ ወያኔ ሃርነት ትግራይ ፖርቲ አባላትና ደጋፊዎች ውግዘት አስከተለበት ። አንዲት የወላጅ መምህራን ህብረቱ አባል ለትምህርት ጥራቱ ንጽጽር “ኤርትራ” የምትባለውን ሃገር ከአፉ ያወጣውን ወጣት ምሁር በአደባባይ ወጥተው ወረፉት። የወላጆችና መምህራን በሆነው ስብሰባ ለምን ይሳተፋል ሲሉም ከስብሰባው እንዲዎጣ ሲሉ በድፍረት እስከመናገር ደርሰው ብዙሃን ተሰብሳቢውን አሳፈሩ :(

ግማሽ ሌሊት በዘለቀው ስብሰባ የሚጨበጥ መፍትሔ ሳይያዝ ተበተነ ። ስብሰባው አብቅቶ ወደ የቤታችን ለመሔድ ከግቢው እንደወጣን ከአዳራሹና ከኮሚኒቲው ግቢ ውጭ ” የተከበሩት ” የድርጅት ሰዎች ወጣቱን ከበው ሲያዋክቡት ደረስኩ ። ምክንያቱን መጠየቅ አላስፈለገኝምና ግርግሩን በአርምሞ መታዘብ ጀመርኩ። ወጣቱን ከመካከል አድርገው ሲያዋክቡት ቁልጭ ቁልጭ እያለ ለሚሰነዘርበት ትችት መልስ ለመስጠት ይሞክራል ። እነሱ ይዝታሉ ፣ ያንቋሽሹታል። ” የትምህርት ንጽጽሩን በተጨባጭ ካየው እውነታ ጋር የመናገር ነውርነቱ ምኑ ላይ ነው? ” የሚሉት በአንጻሩ የባለጊዜወችን ቁጣ በመቃወም በእሰጣ ገባው መካከል ለወጣቱ ድጋፋቸውን መግለጽ ሲጀምሩ ክርክሩ ሜዳ ላይ ለአፍታም ቢሆን ተፋፋመ ። አፍ የፈታበት ትግርኛ ቋንቋ አፉን ያዝ እያደረገው መልስ የሚሰጠውን ወጣት ምሁርን በራስ መተማመን ስመለከት የመቀሌው አብርሃ ደስታ ትዝ አለኝ። ልዩነቱ አብርሃ መቀሌ ላይ በእሳት ውስጥ ሆኖ ስርአት አልበኝነትን የሚቃወም ሆኖ ሳለ ይህኛው ወጣት የሚሞግተው ፖለቲከኛ ሆኖ ስለፖለቲካና ኢ ፍትሃዊ አስተዳደር እያወራ አለመሆኑ ነው። ወጣቱ በ3000 ታዳጊዎች የትምህርት ማዕከል ላይ የሚታየውን የአስተዳደር ኢ ፍትሃዊነትና የትምህርት ጥራት አለመኖር በድፍረት በመናገሩ በወንዙ ልጆች ዘንድ ” አይንህን ላፈር ” አስብሎ በእርጉም አስፈርጆታል ። ግርግሩ በረድ ሲል ወጣቱ ወደ ቤቱ ለመሄድ ከአንድ ወዳጀ ጋር የሚያደርሳቸው ሲያፈላልጉ አየኋቸውና እግረ መንገዴን ላድርሳቸው ጠራኋቸው። ወጣቱ ኢኮኖሚስትና “አላጠፋም አትንኩት! ” ሲል ይሞግትለት የነበረው ወዳጀ ከእኔው ጋር ተሳፍረው መጓዝ ጀመርን … እናም ከሰላምታ በኋላ እኔ እንደለመደብኝ መጠየቅ እሱም መመለስ ያዘ …

ገና ልጅ እግር ነው ። እድሜው ከሃያዎቹ አያልፍም። በ1990 ዎቹ ከትግራይ ክልል ተነስቶ በአዳማ ዩኒቨርሲቲ ዘመነኛውን የኢኮኖሚክስ አስተዳደር ትምህርት ለስድስት አመታት ተከታትሎ በማዕረግ ተመርቋል ። ከ2000 ዓም ወዲህ በትምህርቱ የላቀ ውጤት በማምጣቱም እዚያው አዳማ ለስድስት አመታት ዩኒቨርሲቲ አስተምሯል ። በሃገር ቤት የኑሮ ውድነት ጣራ ነክቶ አልመቸህ ቢለው ባንድ ክፉ ቀን ከስራ ባልደረቦቹ ጋር ወደ ውጭ ሃገር ሄደው በስደት የተሻለ ገቢ አግኝተው በሚሰሩት ሁኔታ ዙሪያ ተመካከረ። “በሳውዲ በኩል ወደ ሌላ አውሮፖ ሃገር መውጣት ይቻላል!” የሚባል መረጃ ለእርሱና ለጓደኞቹ ስለደረሳቸው በአሳር በመከራ ያጠራቀሟትን ጥሪት በመሰባሰብ ቪዛ ገዝተው ከአመት በፊት ወደ ሳውዲ ጅዳ ከተፍ አሉ።

… ሳውዲ አረቢያ ግን እነሱ እንዳሰቧት ሆናም ሆነ ወደ አውሮፖ የሚደረገው ስደት የቀለለ አለመሆኑን የአረቦቹን ኑሮ በተቀላቀሉ ቅጽበት ማገናዘብ ቻሉ ። በቃ እሱና ጓደኞቹ ሳውዲን እንዳሰቡት አላገኟትምና ብዙ ሳይቆዩ በጅዳ የተለያዩ አካባቢዎች እየተዘዋወሩ ስራ ፍለጋ ጀመሩ … በሰው በሰው በጅዳ የኢትዮጵያ አለም አቀፍ ትምህርት ቤት ” የመምህራን እጥረት አለ !” ሲባል ሰምተው ከአንድ ጓደኛው ጋር ወደ ትምህርት ቤቱ አስተዳደር በመሄድ የትምህርት መረጃቸውን አቀረቡ። ምንም እንኳን ትምህር ቤቱ ካላቸው ከፍተኛ የትምህርት ደረጃ አንጻር ባይመጥናቸውም እንደ ዜጋ ዝቅ ብለው ለመስራት እና ለዚህ ትውልድ እውቀታቸውን ለማካፈል እድል አገኘን ብለው ያቀረቡት አቤቱታ ግን በትምህርት ቤቱ አስተዳደር በኩል ለውድድር ቀርበው ግልጋሎት መስጠት የሚችሉበት እድል የተነፈጋቸው መሆኑን ወጣቱ አጫወተኝ ! ይህ ወጣት ምሁር አክሎ እንዳጫወተኝ ከሁሉም የሚያስገርመው የ11 ኛ እና የ12 ኛ ተማሪዎችን በኢኮኖሚክስ ያልተመረቀ መምህር ታዳጊዎቹን በሚያስተምርበት ትምህርት ቤት እንዴት በሙያው የተካንን ፣ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በዩኒቨርሲቲ የማስተማር ብቃት ያለው ዜጋ ዝቅ ብየ ላስተምር ሲል እንዴት እድሉን ይነፈጋል ? ሲል የሚያጠይቀው ወጣት የትምህርት መረጃዎችን ተቀብሎ ማወዳደር መጠየቅና ተገቢውን ለታዳጊዎች የሚጠቅም እርምጃ መውሰድ ሲገባ ” ስትፈለጉ እንጠራችኋል! ” በሚል መልስ መሸንገላቸውን በስሜት ገልጾልኛል!

“በዜጎች ላይ አንቀልድ ፣ በነገ የሃገሪቱ ተስፋዎች ልንቀልድባቸው አይገባም ” ሲል ስሜትን በሚነካ መንገድ የገለጸልኝ ይህ ወንድም በአሁኑ ሰአት የተለያዩ ተማሪዎችን በየቤታቸው እየሄደ በማስተማር ትምህርት ቤቱ ሊከፍለው ከሚችለው ገንዘብ በላይ ገቢ እንዳለው የገለጸልኝ ሲሆን ያም ሆኑ ትምህርት ቤቱ ለመደገፍ ይቻል ዘንድ ባለው ትርፍ ጊዜ መምህራን እንዴት ራሳቸውን ብቁ አድርገው ማስተማር እንዳለባቸው የተለያዩ ትምህርት ማጎልመሻ ስልጠናዎችን በነጻ ለመስጠት ከጓደኞቹ ጋር ጥያቄ ቢያቀርብም ትምህርት ቤቱም ሆነ ለባለቤት ተብየው ለጅዳ ኮሚኒቲ ያቀረበው አቤቱታ ተቀባይነት እንዳላገኘ በቁጭት አጫውቶኛል። እስኪ እሰበው ” ዜጎችን እንደግፍ ስንል ለምን እድሉ አይሰጠንም ? ” በማለት ያጠይቃል ! ወጣቱ እውነት አለው !

3000 ታዳጊዎች የምናስተምርበት ትምህርት ቤት ባልረባባ ምክንያት በአደጋ ላይ እንዳለ በስብሰባው በግልጽ ተመልክቷል። የመምህራንን እጥረትን መሰረት አደረገ የሚባለው የትምህርት ጥራት እያደረ ማሽቆልቆል በስብሰባው በአደባባይ በወላጅ እና መምህራን ህብረቱ ፣ በስብሰባው ተሳታፊ ወላጆች እና በመምህራን በግልጽ ተነግሮናል። ይህ የአደባባይ ሚስጥር ሆኖ እያለ ለትምህርት ጥራቱ ማሽቆልቆል የመምህራን እጥረት ምክንያት በሆነበት የትምህርት ማዕከል የላቀ እውቀት ያላቸው አቤቱታ ወገኖች አቤቱታ ለምን ተፈነገለ ? የ11ኛ እና የ12 ኛ ክፍል ወሳኝ ክፍሎች ለምን አዋቂ ሳይጠፋ እውቀቱ በሌላቸው መምህራን እንዲማሩ ማድረግ ለምን አስፈለገ ? በዚህ መሰል አስተዳደር የሚመራው ትምህርት ቤት የትምህርተ ጥራቱን አስጠብቆ ልጆቻችን ወደ ተሻለ የእውቀት ጎዳና ያደርሳቸዋል ብሎ ማሰብስ እንዴት ይቻላል? ለዚህ ጥያቄ መልስ መስጠት ያለባቸው ወጣቱን በመረጃ በአደባባይ መሞገት ያልቻሉት ወገኖች እና አጫፋሪዎቻቸው ቢሆኑ ደስ ይለኛል ። ኤርትራ የምትለው ሃገር ስለተነሳች ያንገበገባቸው ወገኖች ንጽጽሩ ከሱዳን አለያም ከፖኪስታን ተማሪዎች ጋር ቢሆን እንዲህ ያንገበግባቸው ነበርን ? ጉዳዩን በቅንነት ማሰብ ከቻሉ ኤርትራን የምትለውን ቃል ትተው የትምህርት ጥራት የለም ለሚለው የወጣቱና የብዙሃን ወላጅ አስተያየት ለምን በአደባባይ ምላሽ ሊሰጡ አልቻሉም ? ለነገሩ ይህንን ለማድረግ ሞራል የላቸውምና አልፈርድባቸውም ። እኔም ቢያንስ ከዚህ ተነስቸ ይህንን ደረቅ እውነት ለመገምገም የተለየ ክህሎት ይጠይቃል ብየ ስለማላምን በማለዳ ወጌ ተነፈስኩት …
ቸር ያሰማን
ነቢዩ ሲራክ

አንድ ቁምነገር፤ የብሄራዊ ቋንቋ ያለህ…!!! –ከአቤ ቶኪቻው

$
0
0

በነገራችን ላይ ብሄራዊ ቋንቋ የሚባል ነገር የለንምኮ… አማርኛ ለረጅም ጊዚያት የሀገሪቱ ብሄራዊ ቋንቋ ሆኖ አግልግሏል። አሁን ግን አማርኛ በአማራ ክልል እና በፊደራል አስተዳደሮች (አዲስ አበባ እና ድሬደዋ እንዲሁም ይሁንልን ባሉ አንዳንድ ከልሎች) ብቻ ተውስኖ ይኖር ዘንድ ተፈርዶበታል። ሁሉም ክልሎች ውስጥ የሚኖሩ ተማሪዎች በገዛ አፍ መፍቻ ቋንቋቸው ይማራሉ። እንዲሁም እንደየ ክልሎቹ ሁኔታ ‘የፌደራሉን’ ቋንቋ (አማርኛ) ከተወሰነ ክፍል በኋላ መማር ይጀምራሉ። (የፌደራል ቋንቋ ስል የፌደራል ፖሊስ ቋንቋ ማለቴ አይደለም ካነሳናቸው አይቀር ግን የእነርሱ ቋንቋ ራሱ መቀየር እንዳለበት ጠቁሞ ማልፉ መልካም ነው እስከመቼ ድረስ ቆመጥ እና ክላሽ ለመግባቢያ ቋንቋ ይጠቀማሉ… ) ሃሃ… ብለን ወደ ቁምነገራችን ስናሳልጥ፤

school
በግሌ ተማሪዎች በአፍ መፍቻ ቋንቋቸው መማራቸውን አሳምሬ እደግፈዋለሁ። በአፍ መፍቻ ቋንቋ አለመማር አቀበቱ ብዙ ነው። ለምሳሌ፤ አንድ በጉራግኛ አፉን የፈታ ልጅ በሳይንስ ትምህርት ክፍለ ጊዜ በቅጡ በማይርዳው ቋንቋ የእጅ መታጠብ ጥቅም ቢነገረው ቋንቋውን ለምዶ መምህሩ ምን እያለው እንደሆነ እስኪገባው ድርስ ፊቱን ሳይታጠብ ወደ ትምህርት ቤት ሊመጣ ነው ማለት ነው። ስለዚህ በአፍ መፍቻ ቋንቋ መማርን ድሮ አርስናልን እድግፍ ከነበረው በላይ የምደግፈው ነገር ነው። (እኔ የምለው አርሴ ገሰገሰች…. አሁንም ድጋፌን ለጅምርላት ወይስ አርፌ ሲቲዬን አይዞሽ… ልብል…)

ያም ሆኖ ግን ኢትዮጰያን የመሰለች ሀገር፤ እንዴት ብሔራዊ ቋንቋ አይኖራትም… ይሄን ጊዜ አንስተኛ እና ጥቃቅን የኢህአዴግዬ ካድሬዎች “ኢትዮጵያ የሚባል ብሄር ስለሌለ ኢትዮጵያ ብሄራዊ ቋንቋ አያስፈልጋትም” ሊሉ እንደሚችሉ ይጠረጠራል ተጠርጥሮ ታድያ እንዴት ዝም ይባላል…

አሁን ‘በስራ’ ላይ የሚግኘው የኢትዮጵያ ህግ መንግስት፤ አንቅጽ አራት ላይ የኢትዮጰያ ብሄራዊ መዝሙር፤ በሚለው ርዕስ ስር “የኢትዮጰያ ብሔራዊ መዝሙር የህገ መንግስቱን ዓላማዎችና የኢትዮጵያ ሕዘቦች በዴሞክራሲ ስርዓት አብረው ለመኖር ያላቸውን እምነት፤ እንዲሁም የወደፊት የጋራ ዕድላቸውን የሚያንፀባርቅ ሆኖ በሕግ ይወሰናል።” ይላል። ይህም ሕግ መንግስቱ ራሱ ኢትዮጵያዊ ብሄርተኝነት መኖሩን ያመለክታል ማለት ነው። ስለዚህ ኢህአዴግ መስተፋቅር እና መስተ ነዋይ ያስነካቻችሁ በሙሉ “ኢትዮጵያዊ ብሄርትኝነት የለም” ስትሉ ከህገ መንግስቱ ጋር እየተላተማችሁ እንድሆነ ታውቁት ዘንድ ይሁን፤ (መላተም ብርቃችን አይደለም ካላችሁንም እንግዲህ በቴስታ በሉትና የግንባራችሁን ታገኛላችሁ!)

ሀገር በብሔራዊ መዝሙር ብቻ አትኖርም በብሄራዊ ቋንቋም እንጂ… ብለን በአዲስ መስመር ስንቅጥል፤

አሁንም ህግ መንግስቱን ስናየው፤ አንቅጽ አምስት ላይ ስለ ቋንቋ ሲደነግግ፤ “ማናችውም የኢትዮጵያ ቋንቋዎች በእኩልነት የመንግሥት እውቅና ይኖራችዋል” ይላል… እስይ የኔ አንበሳ ብለን ስንወርድው፤ በዚሁ አንቅጽ ቁጥር ሁለት ላይ “አማርኛ የፌድራሉ ቋንቋ ይሆናል” ይላል። እዚህ ላይ ነው እንግዲህ የምንቀውጠው፤ (አራዳ “ቀወጠው” ብሎ ሲል፤ አጥብቆ ተከራከረ አለቀም እምቢኝ አለ፣ በጉዳዩ ላይ ያዙኝ ልቀቁኝ ሲል ተጨቃጨቀ። የሚል ትርጉሜ ይይዛል።)

“አማርኛ የፌደራሉ የስራ ቋንቋ ይሆናል” ሲል የደነገግውን ሕገ መንግስት አፍ ካለው ይናገር ዘንድ ከሌለውም በተወካይ በኩል እንዲመልስልኝ ሁለት ጥያቄዎችን እጠይቀዋለሁ፤ አንደኛው አማርኛ ብቻውን ምን እዳ አለበት እና ለብቻው የፌደራሉ ቋንቋ ይሆናል… የሚለው ሲሆን ሁለተኛ ደግሞ፤ ብሄራዊ መግባቢያ ቋንቋችንስ ምንድን ነው… የሚል ይሆናል።

እንደ ሀገር የሚያስትሳስርን የሚያግባባን ሁለትስ፣ ሶስትስ ቋንቋ ቢኖርን የሚጎዳው ማነው… በባቢሎን ዘመን ስራ ፈቶች እግዜርን ላይ ለመድርስ ግንብ ሲገነቡ የልባቸውን ክፋት ያየው አምላክ ቋንቋቸውን ደበላልቀው የሚል ሃይማኖታዊ ትምህርት ሰምቼ አውቃለሁ፤ ታድያ መንግስታችን በልባችን ምንም ክፋት የሌለብንን ዜጎቹን በቅጡ ተግባብተን በቅጡ ተባብረን ትልቅ ሀገር ብንገንባ ምን ይጎድልበታልና ብሔራዊ ቋንቋ አሳጣን…. (የጥያቄ ምልክት በብዛት)

እናም፤ ጆሮ ያለው ይስማ አንድ የሚያደርጉን ቋንቋዎች ያስፍልጉናል። ሶስት እና አራት ቋንቋዎቸን ብብሔራዊ ቋንቋ ደርጃ የሚጠቅሙ ሀግሮች ተጠቀሙ እንጂ አልተጎዱበትም። ስለዚህ እየተግባባን እንድንገነባ ዛሬውኑ ብሔራዊ ቋንቋዎቻችንን አሳውቁን እና አስትምሩን፤ የዚህ ቁምነገር ፀሀፊ፤ አንጅት ላይ ጠብ በሚሉ አጥጋቢ ምክንያቶች፤ ቢያንስ አማርኛ እና ኦሮምኛ የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቋንቋ ሆነው ግልጋሎት መስጥት እንዲጅምሩ በብርቱ ይውተውታል።

ተቃዋሚዎች ሰምታችኋል!

በሙስና ተጠርጥረው የሚፈለጉት ጌቱ ገለቴ ክስ በሌሉበት እንዲታይ ተወስነ

$
0
0

Getu Gelete
በተጠረጠሩበት የሙስና ወንጀል ተፈልገው በጋዜጣ ጥሪ የተደረገላቸው የ“ጌታስ ኢንተርናሽናል” ከፍተኛ ባለአክሲዮን አቶ ጌቱ ገለቴን ጨምሮ ሌሎች ያልተያዙ ተጠርጣሪዎች፣ በጥሪው መሰረት ባለመቅረባቸው ፍ/ቤቱ ጉዳያቸው በሌሉበት እንዲታይ ሰሞኑን ብይን የሰጠ ሲሆን ችሎቱ የእነ አቶ መላኩ ፈንታን ጉዳይም ተመልክቷል፡፡

ሐሙስ ዕለት የዋለው ችሎት፤ ጉዳያቸው በሌሉበት እንዲታይ ትዕዛዝ ያስተላለፈባቸው አቶ ጌቱ ገለቴን ጨምሮ የገቢዎችና ጉምሩክ ሰራተኞች አቶ ታደሠ ፈይሣ፣ ገዳ በሽር እና ነጋ ቴኒ የቀረበባቸው ክስ፤ ከቀረጥና ታክስ መቀነስና ማስቀነስ ጋር የተያያዘ መሆኑ ይታወሳል፡፡

በእለቱ በቀጠሮአቸው መሠረት ችሎት፣ የቀረቡት፤ የቀድሞ የገቢዎችና ጉምሩክ ዋና ዳይሬክተር አቶ መላኩ ፈንታ እና ምክትላቸው አቶ ገ/ዋህድ ወ/ጊዮርጊስን ጨምሮ በመዝገቡ የተካተቱ ከፍተኛ ኃላፊዎች እና ባለሃብቶች፤ የክስ መቃወሚያቸውን ያቀርባሉ ተብሎ የተጠበቀ ቢሆንም አንዳንዶቹ አልደረሰልንም በማለታቸውና ተጨማሪ 10 ቀን በመጠየቃቸው፣ ፍ/ቤቱ ጥያቄያቸውን ተቀብሎ የሁሉንም ተከሳሾች መቃወሚያ ለመስማት ለየካቲት 10 ቀን 2006 ዓ.ም ቀጥሯል፡፡

በሌላ በኩል የቀድሞ የደህንነት ኃላፊ በነበሩት በአቶ ወ/ሥላሴ መዝገብ፣ ህገወጥ ሃብት ይዞ መገኘት በሚል የተከሰሱ ተከሳሾች ላይ አቃቤ ህግ ክሴን ላሻሽል በማለቱ ክሱን አሻሽሎ እንዲያቀርብ ለየካቲት 3 ቀን 2006 ዓ.ም ቀጠሮ ተሰጥቷል፡፡

(ምንጭ፡ አዲስ አድማስ ጋዜጣ)

Hiber Radio: ኢትዮጵያ በቅርቡ የመፈራረስ አደጋ ከተጋረጠባቸው የአፍሪካ አገሮች ተርታ መሆኗ ተገለጸ

$
0
0

የህብር ሬዲዮ የካቲት 2 ቀን 2006 ፕሮግራም

ጋዜጠኛ ሃብታሙ አሰፋ

ጋዜጠኛ ሃብታሙ አሰፋ

>

አቶ ዳንኤል ተፈራ የአንድነት የድርጅት ጉዳይ አላፊ ከቃሊቲ መልስ ለህብር ከሰጡት ቃለ መጠይቅ የተወሰደ(ሙሉውን ያዳምጡት)

* በሳውዲ የሶስት ሹህ ኢትዮጵያውያን ተማሪዎች ዕጣና የመምህራኑ የስራ ማቆም አድማ ቀጠሮ (ጋዜጠኛ ነብዩ ሲራክ በስፍራው የታዘበው ሙሉ ዘገባ)

የካቲት 12 የጣሊያን ፋሺስት በአዲስ አበባ ጭፍጨፋ ያካሄደበት ቀን ታስቦ ሲውል እንደ ቬጋስ ሁሉ በዓለም ላይ በሰላሳ ከተሞች ይከበራል (አቶ ኪዳኔ አለማየሁ የዓለም አቀፍ ሕብረት ለፍትሕ የኢትዮጵያ ጉዳይ ዋና ዳይሬክተር )

ሌሎችም ዝግጅቶች

ዜናዎቻችን

ኢትዮጵያ በቅርቡ የመፈራረስ አደጋ ከተጋረጠባቸው የአፍሪካ አገሮች ተርታ መሆኗ ተገለጸ

በእስር ላይ የሚገኙት አቶ አስራት ጣሴ ከቃሊቲ እስራቸውን ለኢትዮጵያ ሕዝብ ከምከፍለው መስዋዕትነት ትንሹ ነው አሉ

ጠበቃቸው ነገ ይግባኝ ይጠይቃሉ

* በትግራይ የአረና ስራ አስፈጻሚ ተይዘው እየተደበደቡ መሆናቸው ተገለጸ

* አብርሃ ደስታ ከመቀሌ ህወሃት የደርግን ስርዓት እየደገመ መሆኑን አስታወቀ

* ሰሞኑን በኬኒያ ታስረው ደብዛቸው ጠፋ የተባሉትን የኦሮሞ ተወላጆች ጉዳይ እንዳሳሰበው አንድ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅት ገለጸ

* በአባይ ጉዳይ ከኢትዮጵያ ጋር ዳግም አልወያይም ያለችው ግብጽ ነገ ልኡካኖቿ አዲስ አበባ ይገባሉ

* በሳውዲ የሶስት ሺህ ኢትዮጵያውያን ተማሪዎች ዕጣ አሳሳቢ ሆኗል

* መምህራኑ የስራ ማቆም አድማ እንደሚያደርጉ አስታውቀዋል

* ኦባማ ኬር በግራ ዘመም መገናኛ ብዙሃን እንደሚባለው አዳዲስ ስራዎችን ገዳይ አለመሆኑ ተገለጸ

ሌሎችም ዜናዎች አሉ

አዲስ አበባ እና ጅማ ሌሊቱን በግድግዳ መፈክሮች ደምቀው አደሩ

$
0
0

ድምጻችን ይሰማ/ሰኞ የካቲት 3/2006

በትናንትናው ሌሊት በተለያዩ የአዲስ አበባ አካባቢዎች እና በጂማ ከተማ በርካታ የግድግዳ ላይ መፈክሮች ተጽፈው ማደራቸው ተዘገበ! በጂማ በራሪ ወረቀትም ተበትኗል!!!

በአዲስ አበባ ወደአስኮ በሚወስደው መንገድ በጀኔራል ዊንጌትና አካባቢው፣ እንዲሁም በጦር ሀይሎች መስመር እስከ ቤተል ድረስ ባሉ ቦታዎች በግድግዳዎች ላይ ተጽፈው ያደሩት እኒሁ መፈክሮች የሰላማዊ ትግሉን መንፈስ የሚያንጸባርቁና የህዝበ ሙስሊሙ መብት እንዲከበር፣ ታሳሪዎችም እንዲፈቱ የሚጠይቁ ነበሩ፡፡ ከተጻፉት መፈክሮች መካከል ‹‹ድምጻችን ይሰማ! ኮሚቴው ይፈታ! ህገ መንግስቱ ይከበር! የታሰሩት ይፈቱ!›› የሚሉት ጎልተው የወጡ መሆኑም ታውቋል፡፡

በተመሳሳይ ሁኔታ በጂማ ከተማም በግድግዳዎች ላይ በርካታ መፈክሮች ተጽፈው ማደራቸው የተዘገበ ሲሆን በከተማዋ ሌሊቱን እጅግ በርካታ በራሪ ወረቀት ተበትኖ ማደሩና የከተማዋ አስተዳደርም በሁኔታው መደናገጡን ማወቅ ተችሏል፡፡

ካሁን ቀደምም በተለያዩ ጊዜዎች ብሶቱን በግድግዳ ላይ ጽሁፎች (ግራፊቲ) ሲገልጽ የቆየው የኢትዮጵያ ህዝበ ሙስሊም ከሁለት አመታት በላይ በሰላማዊ መንገድ ሲታገል የቆየ ሲሆን የተለያዩ የሰላማዊ ትግል ዘዴዎችን በመጠቀምም ለመብቱ መከበር የሚያደርገውን ጥረት ቀጥሏል፡፡
muslim 2

 

muslim

muslim3

yesema dimstachin

yesema

Viewing all 15006 articles
Browse latest View live