Quantcast
Channel: Ethiopian News | ዘ-ሐበሻ | Latest News Provider | News For All
Viewing all 15006 articles
Browse latest View live

ይድረስ ለሚኒሶታ መድኃኔዓለም ምዕመናን፡ የተከፋፈሉት አባቶች 1 አስኪሆኑ ድረስ በአስተዳደር ገለልተኝነት ለመቆየት 7 ምክንያቶች

$
0
0

ቀን፡ 12-12-13
በሥላሴ ስም አንድ አምላክ አሜን።
ይድረስ ለሚኒሶታ መድኃኔዓለም ምዕመናን
ደብረሰላም መድሃኔዓለም ቤተክርስቲያን የተከፋፈሉት አባቶች አንድ አስኪሆኑ ድረስ በአስተዳደር ገለልተኝነት መቆየት ይገባታል!

deb
ምክንያቶች፦
1. የደብራችንን ሰላምና አንድነት ለመጠበቅ ያስችላል።
2. የተከፋፈሉትን አባቶቻችንን ለማቀራረብ በሚካሔደው ጥረት ውስጥ ተሳታፊ ለመሆንና የክርስቲያኖችን ድርሻን ለመወጣት ይጠቅማል።
3. የክርስትና ጠባይ ያልሆኑትን የፖለቲካና የዘረኝነትን ነገር በደብራችን እንዳይኖር ይረዳል።
(ስለአገርና ስለኅዝብ መበደል፣ ስለቤተክርስቲያን ጥቃትና መብት ገፈፋ መናገር ግን ፖለቲካ አይደለም።)
4. በአገር ውስጥም ሆነ በውጪ በማንኛውም አካል በቤተክርስቲያን ላይ አንዲሁም በአገርና በህዝብ ላይ የሚደርሱ በደሎችን ተቃውሞ ድምጽን በነጻነት ለማሰማት ይረዳል።
5. ከሌሎች ቤተክርስቲያናት ጋር መልካም ግንኙነት እንዲኖርና በሕብረት ለማገልገል ያስችላል።
6. የምእመናንን ቁጥር ለማብዛትና የቤተክርስቲያናችንን ሁለንተናዊ እድገት ለማምጣት ያስችላል።
7. ወገናዊነት ሳይኖርና ያለህሊና ወቀሳ እምነትን በነጻነት ለመፈጸም ይጠቅማል።

ከዚህ አንፃር በአሁኑ ሰዓት ዘረኝነት፣ አድሎ፣ሙስና፣ወዘተ ወዳለበትና በቀጥታ በመንግስት በሚታዘዝ አስተዳደር ስር እንሁን የሚሉ ክፍሎች ተሳስተዋል። በደብረ ሰላም ዘረኝነት የለም! ለማንም የፖለቲካ ድጋፍ መስጠት የለም!
ስለሆነም ቤተክርስቲያንህን በመንግስት አመራር ስር ለማድረግ የሚሮጡትን ልትቀድማቸው ይገባል!
ለብዙ አመታት ገንዘብህን ፣ጉልበትህን ፣እውቀትህን ፣ጊዜህንና ላብህን አፍስሰህ እዚህ ያደረስከውን የአምልኮ ቤትህን እንዳትቀማ ተነስ።
የችግሩን መንሰኤና መፍትሄ ልቦናቸው እያወቀ አሳልፈው ሊሰጡህ ባሴሩትንም ‘ካህናት’ ላይ ርምጃ ልትወስድ ይገባል።

ለቤተክርስቲያን አንድነት እና ሰላም ከቆሙ ምዕመናን።


የራስን እድል በራስ መወሰን፣ እርስ በርስ እስከማጣላት…ሌላው ኢትዮጵያዊ የተዋረደበት፤ የብሄር ብሄረሰቦች ቀን –በኦጋዴን!

$
0
0

የራስን እድል በራስ መወሰን፣ እርስ በርስ እስከማጣላት…

ሌላው ኢትዮጵያዊ የተዋረደበት፤ የብሄር ብሄረሰቦች ቀን – በኦጋዴን!

ዘንድሮ በኢትዮጵያ ተከበረ የተባለውን የብሄሮች  ቀን ምን ያህሎቻችሁ እንደተከታተላቹህ አላቅም። ላላያችሁት ግንዛቤ ለመፍጠር ያህል… ዘንድሮ በአሉ የተከበረው ሱማሌ ክልል፣ በኦጋዴን ኢትዮጵያ ውስጥ መሆኑን በመንገር ወጋችንን እንጀምራለን። ይህ ዝግጅት እስከዛሬ በትግራይም፣ በአማራውም ክልል ተደርጓል… ሆኖም በአሉ ላይ ሁሉም የየብሄሩን ባህል ለማሳየት ሲጥር እንጂ፤ አንደኛው ብሄር ሌላውን ሲሰድብ ያየንበት አጋጣሚ አልነበረም። የዚህ አመቱ የብሄር ብሄረሰቦች ወይም የብሄረተኞች ቀን ሌላውን ኢትዮጵያዊ በመውቀስ ላይ የተመሰረተ ነበር።

“አማራው፣ ደገኛው፣ የመሃል አገር ሰው…” እያሉ ቀጠሉ አስተያየት ሰጪዎቹ። በአሉን ምክንያት በማድረግ በኮንፈረንሱ ላይ የተገኙት ታዳሚዎች ወቀሳቸውን ቀጠሉ፤ “የመሃል አገር ሰዎች ‘ሽርጣም ሱማሌ’ እያሉ ይጠሩን ነበር” አለ። እኛንም በሃሳብ ወደኋላ መለሰን። የመሃል አገር ሰው ይህንን ቃል አይጠቀምበትም ለማለት አይደለም። ነገር ግን “ሽርጣም ሱማሌ” የሚለውን ቃል መስማት የጀመርነው፤ በኢትዮጵያ እና ሱማሌ ጦርነት ወቅት ነው። “ሽርጣም ሱማሌ” የሚለውን አባባል ሁሉም የመሃል አገር ሰው እንደማይጠቀምበት ሁሉ፤ በቴሌቭዥን መስኮት ላይ ብቅ ብለው ሌላውን ኢትዮጵያ የሰደቡት እና ያሰደቡትም መላውን የኢትዮጵያ ሱማሌ እንደማይወክሉ እናውቃልን። በመሆኑም ይህ ጽሁፍ በሁሉም የኢትዮጵያ ሱማሌዎች ላይ ያነጣጠረ ሳይሆን፤ የማያውቁትን ታሪክ ለማሳወቅ ያህል የተዘጋጀ መሆኑን ልብ ይበሉ።

 (በዳዊት ከበደ ወየሳ –  ጋዜጠኛ)

ethiopia somalia
በ1969 ዓ.ም. ሱማሌ ኢትዮጵያን ስትወር፤ እጅግ በርካታ ኢትዮጵያውያንን አፈናቅለዋል፤ ገድለዋል፤ በሺህ የሚቆጠሩትን ማርከው ወስደው አገራቸው ውስጥ አስረዋል። ሱማሌዎች ይህንን በሚያደርጉበት ወቅት ታዲያ ሽርጥ እንጂ ሱሪ ታጥቀው አይደለም። በዚያን ወቅት ታዲያ የኢትዮጵያ ልጆች ዳር ከዳር “ሆ” ብለው ሲነሱ፤ በወገናቸው ላይ የደረሰው በደል ቢያንገበግባቸው፤ “ይሄ ሽርጣም ሱማሌ” ብለው ቢሳደቡ ሊገርመን አይገባም። ከዚያ በፊት በነበሩት ጦርነቶች ፈረንጆች ኢትዮጵያን ሲወሩ፤ “ይሄ ሶላቶ” ብለው እንደሚጠሯቸው ጠላት የነበረውን የሱማሌ ታጣቂ “ይሄ ሽርጣም” እያሉ በመፎከር፤ የገባበት ገብተው ደምሠውታል፤ ዳግመኛም የኢትዮጵያን ድንበር እንዳይሻገር አድርገውታል።

በ1970 የሱማሌ ጦር ሙሉ ለሙሉ በኢትዮጵያውያን ብርቱ ክንድ ተደመሰሰ። ከጅጅጋ እና አካባቢው ተፈናቅለው የነበሩት የኢትዮጵያ ሱማሌዎች ወደ ድሮ መንደራቸው ተመልሰው፤ ከሌላው ኢትዮጵያዊ ጋር ሰላማዊ ኑሯቸውን ቀጠሉ። “ሽርጣም ሱማሌ” የሚለውም አባባል እየቀረና እየተረሳ መጣ። ዘንድሮ በሱማሌ ክልል፣ በአሉ ሲከበር…  ሌላው ኢትዮጵያዊ ለሱማሌ ኢትዮጵያ የሰራው ውለታ ተረስቶ፤ የመሃል አገር ሰዎች “ሽርጣም ሱማሌ እያሉ ይሰድቡን ነበር” የሚል የጥላቻ መልዕክት ሲተላለፍ ሰማን።

ሌላው አስተያየት ሰጪ ደግሞ ቀጠለ።  “ድሮ ያስተማሩኝ ሰዎች ስማቸው ‘በቀለ፣ መኮንን፣ በየነ’ ነበር። አሁን ግን ጊዜው ተቀይሯል። አስተማሪዎቻችን ስማቸው መሃመድ እና አብዱል ሆኗል።” በማለት ለኢህአዴግን መንግስት ምስጋና ሲያቀርብ ስንሰማ፤ ጆሯችንን ማመን አቅቶን ተገረምነ። ኢትዮጵያ ውስጥ ትምህርት ሲጀመር፤ የዳግማዊ ምኒልክ ት/ቤት የመጀመሪያ መምህራን የመጡት ከግብጽ አገር ነበር። በኋላም ላይ ከህንድ ድረስ መምህራን እየመጡ አስተምረዋል፤ ወይም አስተምረውናል። በውጭ ሰው ስለተማርን… “ለምን የውጭ ሰው አስተማረን?” ብለን አንቆጭም፤ ይልቁንም ለእነዚህ መምህራን አክብሮት እና ምስጋናችንን እናቀርባለን እንጂ። በሱማሌ የተመለከትነው ግን ከዚህ የተለየ ነበር… እቺም እድሜ ሆና… እነበቀለ፣ መኮንን እና በየነ የሚባል ስም የነበራቸው ኢትዮጵያውያን ስላስተማሯቸው የሚናደዱ ሰዎችን ለማየት በቃን።

ደግሞም አንድ ሌላ እያሳቀ የሚያናድድ ነገር ሰማን። ሌላው አስተያየት ሰጪ እንዲህ አለ። “አካባቢያችን ልጅ ምግብ አልበላም ብሎ ሲያስቸግር፤ ‘አማራ መጥቶ እንዳይበላብህ’ በማለት ልጁ አማራ ሳይመጣበት ቶሎ እንዲበላ እናደርግ ነበር።” አለ።

“ጉድ እኮ ነው የሱማሌ ኢትዮጵያ ህዝብ አማራውን ይህን ያህል ይጠሉት ነበር? ማስፈራሪያስ አድርገውት ነበር?” እያልን ተገርመን ሳናበቃ ይኸው ሰውዬ ንግግሩን ቀጠለ።

“በሌላ በኩል ደግሞ የመሃል አገር ሰዎች (አዲሳባ ያለው ሌላው ኢትዮጵያዊ መሆኑ ነው) ልጆቻቸው ምግብ አልበላም ብለው ሲያስቸግሯቸው፤ “ሱማሌ እንዳልጠራብህ!” ብለው ሲያስፈሯቸው፤ ምግቡን ጥርግ አርገው ይበሉ ነበር።” ሲል ሰማን። አብረውኝ ኢቲቪን ይመለከቱ የነበሩ “የመሃል አገር” ሰዎችን በጣም አሳቃቸው። እርስ በርስ ተያየንና “ሱማሌ እንዳይመጣብህ!” ተብሎ ምግብ ሲበላ የነበረ ከመሃላችን ነበር?” ብሎ ጠየቀ አንዱ…

ሌላኛው “እኛ አያጅቦን ነው የምናውቀው” ሲል ትንሽ አሳቀን።

“ሱማሌ ሳይመጣብህ!” ተብሎ እያስፈራሩ ምግብ ያስበሉት ይፍረደን” በማለት በጉዳዩ ላይ ስቀን ልናልፍ እንችል ይሆናል። ነገር ግን … ለአማራው ድርጅት ‘ቆሜያለሁ’ የሚለው ብአዴን/ኢህአዴግ ነገሩን እንዴት አይቶት ይሆን?

የብሄር በሄረሰቦችን ቀን ምክንያት በማድረግ የሚተላለፈው የጥላቻ አስተያየት አሁንም እንደቀጠለ ነው። ኢቲቪን ከመዝጋታችን በፊት ሌላ አስተያየትም አደመጥን። ሰውየው እንባ እየተናነቃቸው፤ “መናገሻ ከተማችንን አዲሳባን ለማየት እንኳን አይፈቀድልንም ነበር።” ብለው ሲሉ፤ በራስ ተፈሪ መኮንን ዘመን የነበሩ የሱማሌ ፖሊሶች ታወሱን። በወቅቱ በአዲስ አበባ፤ በፖሊስነት ተቀጥረው ሰአት እላፊ እና ጸጥታ የሚያስከብሩት የመጀመሪያ ባለደሞዝ የአዲስ አበባ ፖሊሶች የሱማሌ ኢትዮጵያውያን ነበሩ። እናም “አዲስ አበባን ለማየት እንኳን አይፈቀድልንም ነበር” እያሉ የሚያለቅሱትን አዛውንት አይተን፤  “ወደ አዲስ አበባ መሳፈሪያ ካላጡ በቀር የባቡር መስመር ከተዘረጋ ራሱ፤ መቶ አመት አልፎታል”። በማለት ታዝበናቸው ዝም አልን።

ሌላዋ ሴት ደግሞ ቀጠለች። ሴትዮዋ መናገር ስላለባት ብቻ የምትናገር ነው የምትመስለው… “የድሮ እና የአሁኑን ሳስተያየው በጣም ብዙ ልዩነት አለው” ብላ ጀመረች። ልጅቷ እንኳንስ ስለቀዳማዊ ሃአይለስላሴ ዘመን ቀርቶ ስለደርግ ለማውራት እድሜዋ የሚፈቅድላት አይደለችም። ወሬዋን ግን በድፍረት ቀጠለች። “የድሮና የአሁኑ በጣም ልዩነት አለው… ዑውውውው።” በማለት የአሁኑን አዳነቀች። አድናቆቷን ሳታቋርጥ “የድሮ እና የአሁኑን ልዩነት ለመግለጽ ቃላቶች ያጥሩኛል” ብላ በቃላት እጥረት ምክንያት ልዩነቱን ሳትነግረን ቀረች።

ሌላው ደግሞ እንዲህ አለ። “ይሄ አካባቢ ለወታደራዊ ጦር ካምፕ ይጠቀሙበት ነበር እንጂ፤ ለህዝቡ ግድ አልነበራቸውም።” አለን። እውነት ነው። ፈረንሳይ ከጅቡቲ አልፋ ወደ ኢትዮጵያ የመስፋፋት ብዙም ህልም አልነበራትም። እንግሊዝ እና ጣልያን ግን… ሁለቱም ከሱማልያ ግዛቶቻቸው ተነስተው፤ ኦጋዴን እና አካባቢውን ጨምረው እስከ ሃረር ድረስ ለመግዛት፤ ግልጽ የሆነ እቅድ እና ሙከራ አድርገው ነበር። ሱማሊያ ነጻ ከወጣች በኋላ ደግሞ ከራሽያ ባገኘችው የጦር መሳርያ በመታገዝ እጅግ ከፍተኛ ወታደራዊ እንቅስቃሴ አድርጋለች። በዚህ ጊዜ ሁሉ ሰራዊቱ ከመሃል አገር እየተነሳ፤ ኦጋዴን እና አካባቢው በውጭ ሃይሎች ስር እንዳይወድቅ ወታደራዊ እንቅስቃሴዎች ተደርገዋል። ይህ ሌላውን አገር በወታደራዊ ኃይል የመከላከል ስራ… ዛሬ ስሙ እና ውለታው ተረስቶ “አካባቢውን የወታደር ካምፕ አደርገውብን ነበር” በሚል ወቀሳ መቀየሩ ይገርማል።

አብረውን የነበሩት ጓደኞቼ በኢቲቪ ተናደዋል።  ቴሌቪዥኑን ከመስበራቸው በፊት በሰላም ዘጋነውና ሰላማዊ ጨዋታችንን ጀመርን። “ለመሆኑ ሌላው ኢትዮጵያዊ ደገኛ፣ የመሃል አገር፣ ክርስቲያን፣ አማራ…” እየተባለ ቅጽል እየወጣለት መሰደብ አለበት ወይ? ይህ ደገኛም ሆነ ነፍጠኛ ያሉት ኢትዮጵያዊ ለዚያ ህዝብ ውለታ አላደረገምን? ዝርዝር ውስጥ አንገባም። ሆኖም በታሪክ ቅኝት ወደኋላ መለስ ብለን የእውነትን ማህደር በማገላበጥ ታሪክን እስኪ እንመርምር። እንዲህ ነው።

ወደ አጼ ምኒልክ ዘመን እንሂድ… በፊት በቱርኮች፤ በኋላ ደግሞ በግብጾች ሲተዳደር የነበረው ህዝብ የጠመንጃውን አፈሙዝ በኢትዮጵያውያን ላይ አነጣጥሮ እንደነበር ይታወቃል። በ1524 ዓ.ም. ግራኝ አህመድ እና አሊ ኑር እንደገነኑት ሁሉ፤ በ1876 ዓ.ም. ደግሞ አሚር አብዱላሂን ጨምሮ ሌሎች የአካባቢው ገዢዎች ጉልበታቸው የደረጀበት ወቅት ነበር። በወቅቱ ነዋሪውን በቁጥጥራቸው ስር አውለው፤ “በክርስቲያን መንግስት አንገዛም” ማለታቸው እንደተጠበቀ ሆኖ፤ ከዚያ እምነት ውጪ የነበሩትን የገደሉበትና ያጠፉበት ታሪክ ነው ያለን። (ይህም በአረብኛ ተጽፎ የሚገኝ ሰፊ ታሪክ ያለው ጉዳይ ነው) አሚር አብዱላሂም ቢሆን፤ ለአጼ ምኒልክ “አልገብርም” ማለት ብቻ ሳይሆን፤ “አንተም እንደኛ ካልሰለምክ በስተቀር፤ በክርስቲያን ንጉሥ አንገዛም” በማለት ለአጼ ምኒልክ፣ ሽርጥ፣ መቁጠርያ እና መስገጃ ምንጣፍ ነበር የላከላቸው።

አጼ ምኒልክ የተላከላቸውን ሽርጥ፣ መቁጠሪያ እና መስገጃ አብረዋቸው ለነበሩ ሙስሊሞች ሰጥተው፤ ፊታቸውን ወደምስራቅ ኢትዮጵያ አዙረው፤ በአሚር አብዱላሂ የሚመራውን ጦር፤ ጨለንቆ ላይ ገጠሙት። በዚያ የጨለንቆ ጦርነት በርካታ ኢትዮጵያውያን አለቁ። ከሚንልክ ጋር የነበሩ የአማራ ተኳሾች እና የኦሮሞ ፈረሰኞች፤ የአሚር አብዱላሂን ጦር አሸነፉት። ጥር 18 ቀን፣ 1879 አካባቢው በምኒልክ ጦር ነጻ ወጣ። አሚር አብዱላሂም በጅጅጋ አድርጎ አገር ጥሎ ጠፋ።

በኋላ ላይ የአሚር አብዱላሂ ዘመዶች ወደምኒልክ ዘንድ መጥተው፤ “እባክዎን አገሩን እንዳያጠፉት” ቢሏቸው፤ “እኔ አገር አቀናለሁ እንጂ አላጠፋም። እዚህ ድረስ የመጣሁትም ሃይማኖት ለማጥፋት አይደለም። ሁሉም ሰው እንደየ እምነቱ ያድራል።” ብለው ወደጀጎል በሰላም ሲሸኙዋቸው፤ ከነሱም ጋር እነበጅሮንድ አጥናፌ እና እነሻቃ ተክሌ የኢትዮጵያ ሰንደቅ አላማ ይዘው ሀረር ገቡ። ከዚያ በኋላ አካባቢው በርግጠኝነት የኢትዮጵያ ግዛትነቱ ታውቆ፤ በአምስቱም የጀጎል በሮች ላይ የኢትዮጵያ ሰንደቅ አላማ እንዲሰቀል ሆነ። 3ሺህ ወታደሮችም ከራስ መኮንን እንዲቀሩ አድርገው፤ ክልሉ እንደገና በኢትዮጵያ መንግስት ስር ይተዳደር ጀመር።

አጼ ምኒልክ ወደ አዲስ አበባ ሲመለሱ፤ የማረኩትን የግብጽ ወታደሮች አልገደሏቸውም። ይልቁንም ግብጾቹ የአሚር አብዱላሂን ጦር ለማበረታት ወታደራዊ ማርሽ ያሰሙ ነበር። አሁንም የምኒልክ ጦር በድል አድራጊነት ወደ አዲስ አበባ ሲገባ፤ አጼ ምኒልክ እነዚህኑ የጦር ሙዚቀኞች ታምቡር እያስመቱና ጥሩንባ እያስነፉ በወታደራዊ ስነ ስርአት አዲስ አበባ ሲገቡ ህዝቡ ግራና ቀኝ ተሰልፎ በታላቅ ደስታ እና እልልታ ተቀበላቸው። ያንጊዜ ታዲያ ማርከው ያመጡት ግብጾቹን ብቻ ሳይሆን፤ ለማዳ እርግቦች በሽቦ ቤት ያሉ እርግቦች እና ትላልቅ ሰሎግ ውሻዎች ጭምር ነበር። ያኔ ታዲያ እንዲህ ተባለ…

የምኒልክ ነገር፣ ይመስለኛል ተረት፤

አሞራው በቀፎ፣ ውሻው በሰንሰለት።

ይህ የሆነው የካቲት 28፣ 1879 ዓ.ም. ነው። እንግዲህ ሌላው ኢትዮጵያዊ የሚያውቀው እውነት ይህ ሆኖ ሳለ፤ የአካባቢው ሰዎች “ክልላችንን የጦር ካምፕ አደረጉብን” በማለት ምኒልክን እንደጨፍጫፊ እና ተስፋፊ ሲያዩ “እንቁላል ለመጥበስ መጀመሪያ ቅርፊቱን መስበር ያስፈልጋል” ከማለት ሌላ ብዙም የምንለው አይኖርም። ይልቁንስ ከአስር አመታት በፊት ይመስለናል… በዚሁ ኢቲቪ የተመከትነው አንድ ለቅሶ ነበር። ስለኢትዮጵያ አንድነት ሲባል፤ ምኒልክ እና አሚር አብዱላሂ ጦርነት ያካሄዱበት ጨለንቆ ድረስ ሄደው፤ መሬቱን ቆፍረው የሟቾችን አጽም ከመቶ አመት በኋላ በማውጣት፤ “ምኒልክ የጨፈጨፏቸው…” ብለው ደረት እየመቱ ሲያለቅሱና ሲያስለቅሱ አይተን፤ “ወይ ታሪክ!?” ብለን ያለፍንበት አጋጣሚ ተፈጥሮ ነበር።

በሱማሌ ክልል የተከበረው የብሄር ብሄረሰቦች ቀን እና በሌላው ኢትዮጵያዊ ላይ የደረሰው ውርደት ምን ያህሉን ሰው እንዳበሳጨው ለማወቅ ያስቸግራል። እኛ ግን እንላለን… “የአካባቢው ሰዎች ታሪካቸውንና ማንነታቸውን ወይም ታሪካችንን እና ማንነታችንን አያውቁም ማለት ነው። ሰው ሱማሌ፣ ኦሮሞ ወይም አማራ ስለሆነ አዋቂ አይሆንም። አገር እና ብሄር ሰውን አይለውጥም፤ ትምህርት ግን ሰውን ይለውጣል” ስለዚህ አሁንም ትንሽ ወደኋላ መለስ ብለን የጋራ ታሪካችንን እንጨዋወት፤ በዚያው እንማማር፤ እንለወጥ።

እንደ እውነቱ ከሆነ፤ ይህ አካባቢ ከጥንት ጀምሮ በኦሮሞ ኢትዮጵያውያን ተይዞ የነበረ ክፍለ ግዛት ነው። በ10ኛው ክፍለዘመን የሱማሌ ነገድ ከታጁራ ቤይ ተነስቶ መስፋፋት ሲጀምር የኦሮሞን ህዝብ እየተገፋ፤ በዋቢ ሸበሌ እና ጁባ ወንዝ መሃል በሚገኘው ቤናዲር በሚባለው ቦታ ላይ እንዲቆይ አድርጎት ነበር። በኋላም ኦሮሞዎቹን… ከታች የባንቱ ህዝብ ከላይ ሱማሌ ሲያስቸግራቸው ወደ ወላቡ፣ አበያ፣ ባሌ ድረስ ዘልቆ ራሱን በገዳ ስርአት እያደራጀ ቆይቶ፤ የግራኝ አህመድ ልጅ ወራሽ የሆነውን አሊ ኑርን ሐዘሎ ላይ ገጥሞ በ1551 ዓ.ም. እስከሚደመስሰው ድረስ በመሃል ብዙ ታሪኮች አልፈዋል። ከ10ኛው እስከ20ኛው ክፍለ ዘመን ድረስ አካባቢው በዚህ አይነት ምስቅልቅል ውስጥ ነው የቆየው።

በኢትዮጵያ ክልል ውስጥ የነበረው ምስቅልቅል እንዳለ ሆኖ፤ በተለያዩ ጊዜያት ከሱማልያ ግዛት የጦር መሳርያ ይዘው በመግባት፤ የኦሮሞውን ህዝብ በመግደል እና ከብቱን በመዝረፍ፤ ህዝቡን በማፈናቀል ብዙ ግፍ ተሰርቷል። እንደ እውነቱ ከሆነ ይህ ክልል፤ በሌሎች ላብ እና ደም የተገነባ ክልል ነው። ይህን በማለት ወደኋላ ተመልሰን የምንቀይረው ነገር የለም። ሆኖም የማያውቁትን ወይም እያወቁ ሊያውቁ የማይፈልጉትን አንዳንድ ነገሮች ብናስታውሳቸው ክፋት የለውም።

በምኒልክ ዘመን ከተፈጠሩት አኩሪ ገድሎች መካከል የአድዋ ጦርነት አንደኛው ነው። ይህ ጦርነት የካቲት 23 ቀን 1888 ዓ.ም. በድል ከተጠናቀቀ በኋላ፤ በጦር ተማራኪዎች ላይ እርምጃ እንዲወሰድ ምኒልክ ዘንድ ምርኮኞችን አቀረቧቸው። ምኒልክ ምርኮኞች እንዲገደሉ አላደረጉም። ፈረንጅ ተማራኪዎችን ወደ አዲስ አበባ ይዘው ሲመለሱ፤ በኤርትራ እና በሱማሌ ተወላጆች ላይ ለየት ያለ ፍርድ ሰጡ። “ከአውሮፓ ወራሪ ጋር ሆነው የገዛ ወገናቸው ላይ ጥይት መተኮሳቸው ያሳዝናል። አሁንም ቀሪው ህዝብ እነሱን እያየ እንዲማር፤ ተንበርክከው የተኮሱበት ግራ እግራቸው እና ቃታ የሳቡበት ቀኝ እጃቸው ይቆረጥ።” ብለው ፈረዱ እንጂ አልገደሏቸውም።

ወደ አሁኑ የሱማሌ ክልል ልውሰዳቹህ። አካባቢው በ1879 ነጻ ከወጣ በኋላ ህዝቡ በሰላም መኖር ቢጀምርም፤ ኦሮሞዎቹ መሬት እና ከብታቸውን መነጠቃቸው ሊቆም አልቻለም። በወቅቱ የነበሩት የአካባቢው ኦሮሞዎች በተደጋጋሚ በሚደረግባቸው የድንበር ውጊያ ምክንያት ከብቶቻቸውን እየተዘረፉ፤ መሬታቸውን እየተነጠቁ፤ የሞቱት ሞተው፤ የቀሩት አካባቢውን እየለቀቁ ወጡ።  ባለንበት ዘመን ደግሞ ሰዎቹን ብቻ ሳይሆን የሰጡትን ስያሜ ጭምር ሊቀይሩት ሲጥሩ ተመለከትን። ለምሳሌ “ጅጅጋ” ማለት በኦሮምኛ “ዝቅ ዝቅ” እንደማለት ነው (የአካባቢው ከፍታ ዝቅ ያለ በመሆኑ የተሰጠ ስያሜ ነው)። ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ግን “ጅጅጋ” ማለታችውን ትተው “ጅግጅጋ” በሚል መጤ ስያሜ ለመቀየር እና አዲስ ስም ለመስጠት የሚሯሯጡ ሰዎችን ታዝበናል።

የቅርቡን ታሪክ ትተን… እንደገና ወደኋላ እንመለስ። ይህ ሁሉ ግፍ በኦሮሞዎቹ ላይ ሲሰራባቸው፤ ሌሎች ኢትዮጵያውያን ዝም አላሉም። ይልቁንም በራስ መኮንን አስተዳደር ወቅት… የሱማሌ እና የኦሮሞ ህዝቦችን በሚያጣሉት የድንበር ቦታዎች ላይ በሙሉ፤ ነፍጥ የያዙ ወታደሮች ተመደቡ። በኋላ ክልሉን ለቀው ሊሄዱ ሲሉ፤ ህዝቡ እንቢ ብሎ መሬት እየሰጠ፤ ልጆቻቸውን እየዳሩላቸው ኑሯቸውንም እዚያው አደረጉ። እነዚህ ነፍጥ አንጋቾች ወይም ነፍጠኞች…. አብዛኛዎቹ ከሰሜን ሸዋ የተውጣጡ ጎበዝ አልሞ ተኳሾች ነበሩ። ሱማሌው እንደለመደው የኦሮሞውን ከብት እና እርሻ ለመዝረፍ ድንበር እያለፈ ሲመጣ፤ በጥይት እየለቀሙ ስርአት አስያዙት። የ85 አመት አዛውንት የሆኑት  አቶ ሉልሰገድ ጎበና የሚነግሩን ቁም ነገር አለ… ቀደም ሲል በ1879 ምኒልክ ድል ሲያደርጉ እነሻቃ ተክሌን ሰንደቅ አላማ አስይዘው ወደሃረር መላካቸውን ተጨዋውተን ነበር። (የሻቃ ተክሌ ልጆች ደግሞ ፊታውራሪ ዝቅ አድርጌ እና ግራዝማች መኩሪያ ብዙ ታሪክ ያላቸው ጀግኖች ናቸው።) የሻቃ ተክሌ የልጅ፣ ልጅ፣ ልጅ ናቸው - አቶ ሉልሰገድ። በወቅቱ ልጅ ነበሩ። በአያታቸው ጊዜ የነበረውን ሁኔታ ያስታውሳሉ። የነገሩኝን ዝርዝር ታሪክ ሰብሰብ አድርጌ ላስነብባችሁ። እንዲህ አሉኝ… “በኋላ ላይ አያቴ ግራዝማች መኩርያ ተክሌ ወደ ጅቡቲ ድንበር አስተዳዳሪ ሆነው ተመደቡ። ከአፋሮች ጋር ጥሩ ወዳጅ ሆነው ነበር። ሱማሌዎቹ ተደራጅተው ወደ ኢትዮጵያ ሲዘልቁ፤ አፋሮቹ መጥተው ይነግሯቸዋል። ከዚያም ግራዝማች ሱማሌዎቹን እየተከታተሉ ይቀጧቸው ነበር…” እኚህ እና ሌሎች ኢትዮጵያውያን ኑሯቸውን እዚሁ አድርገው፤ እስከ2ኛ የጣልያን ወረራ ድረስ ዘልቀዋል። ከጣልያን ጦርነት በኋላ ኤጄርሳ ጎሩን አስተዳድረዋል። በዚህ አይነት ወልደው እና ከብደው የኖሩትን ሰዎች ነው ታድያ… ዛሬ በብሄር ብሄረሰቦች ሽፋን የሚሰድቧቸው።

“ክልላችንን የጦር ካምፕ አደረጉት” አልነበር የተባለው? እንግዲያው ሌላም ታሪክ እንጨምር። በ1953 ዓ.ም. በዋርዴር እና በገላዲን አካባቢ የሱማሌ ጦር በወገናችን ላይ ጉዳት ሲያደርስ፤ በመልሶ ማጥቃት ዘመቻ የ3ኛ ክፍለ ጦር አንድ ሻምበል ተንቀሳቅሶ ድል ተጎናጽፎ ነበር። በዚያው አመት ጄነራል አማን አምዶም ቡርበርዴን እና ቡክሲን አልፎ ሲመጣ… በጥቂት እግረኛ፣ መድፈኛ እና ፓራ ኮማንዶ ወታደሮች ወሰን አልፈው የመጡ የሱማሌ ወራሪዎችን ደምስሠዋል። ኢትዮጵያውያን በዚህ የኦጋዴን በርሃ የተሰዉት አካባቢውን የጦር ካምፕ ለማድረግ ሳይሆን ህዝቡን ከወራሪ ለመጠበቅ መሆኑን ለማወቅ ዲግሪ መጫን አይኖርብንም። በዚህ የምስራቁን ድንበር በማስከበር ላይ ከተሰማሩት ጀግኖች መካከል፤ በኦጋዴን በርሃ የእድሜውን ማምሻ የጨረሰውን ጀግናው አብዲሳ አጋን መጥቀስ ያስፈልጋል። የሱማሌ ባህል እና ብሄራዊ ማንነቱ እንደተከበረ ሆኖ፤ የኢትዮጵያውያን የህይወት መስዋዕትነት ሊዘነጋ አይገባም።

ዘንድሮ በሱማሌ ክልል የብሄር ብሄረሰቦች ቀን ሲከበር፤ ሌላውን ብሄር በመሳደብ ከሚከበር ይልቅ… ሌላው ብሄረሰብ ለዚህ ክልል ያደረገውን መልካም ነገር በማስታወስ፤ ታሪካቸውን በማወደስ… ሌላውን ኢትዮጵያዊ የሚያከብሩበትና የሚያመሰግኑበት ጥሩ አጋጣሚ ይሆን ነበር። ይህ ግን ሳይሆን ቀረና፤ የትላንቱ ታሪክ ተረስቶ… ጆሯችን የስድብ ውርጅብኝ ለማዳመጥ በቃ።

እሩቅ ባልሆነው በትላንት ታሪካችን… አካባቢው በሱማሌ ወራሪ ሃይል ሲያዝ የነበረውን ሁኔታ በማስታወስ ስንብት እናደርጋለን። በወቅቱ የሱማሌ ጦር ከራሽያ ያገኘው የጦር መሳሪያ ከኢትዮጵያ በአምስት እጥፍ የሚበልጥ ነበር። ይህን ሃይል በመያዝ በምስራቅ በኩል እስከ አዋሽ ያለውን የኢትዮጵያ መሬት ለመያዝ በቅተው ነበር። በገላዲን፣ በጅጅጋ፣ በደገሃቡር፣ በቀብሪደሃር፣ በጎዴ… እስከ ድሬዳዋ ድረስ የሱማሌ ጦር በምድር እና በአየር እየታገዘ ኢትዮጵያን እና ህዝቧን ወርሯል። ይህ ሁሉ ወረራ ሲደረግ ታዲያ… የሱማልያ ጦር ዝም ብሎ… መንገዱ አልጋ ባልጋ ሆኖለት አይደለም የገባው። በያንዳንዱ ግንባር የኢትዮጵያ ወታደሮችን እየገደለ፤ ሰላማዊ የሆነውን የአካባቢውን ነዋሪ እየጨፈጨፈ ነበር – ድሬዳዋ ድረስ የዘለቀው።

እነዚህን ሁሉ አካባቢዎች መልሶ በማጥቃት ወደ ኢትዮጵያ ለመመለስ የተከፈለው መስዋዕትነት ቀላል አልነበረም። በአካባቢው የነበረው 3ኛ ክፍለ ጦር እና የኢትዮጵያ አየር ኃይል የፈጸሙት ታላቅ ጀብዱ ምንግዜም በታሪክ የሚወደስ ነው። F-5 ተዋጊ ጀቶች ከደብረዘይት እየተነሱ የሱማሌን እግረኛ በመትረየስ ሲረመርሙት፤ እግረኛው የኢትዮጵያ ጦር ደግሞ ሱማሌውን እግር በ’ግር እየተከተለ መግቢያ ያሳጣው ነበር። ከአየር ኃይል አብራሪዎች መካከል እነሜ/ጄነራል አምሃ ደስታ፣ ሜ/ጄነራል ፋንታ በላይ፣ ኮ/ል አስማረ ጌታሁን የምስራቅ ዕዝ ዋና አዛዥ ደምሴ ቡልቶ እና ሌሎች… ከምንም በላይ ደግሞ በዚህ ጦርነት ላይ ህይወታቸውን እና አካላቸውን ያጡ በርካታ ኢትዮጵያውያን፤ ለኢትዮጵያ ሲሉ ከየመን የመጡ መድፈኞች እና የኩባ ወታደሮች ጭምር፤ የከፈሉትን መስዋዕትነት ለአንድ አፍታም ቢሆን ልንዘነጋው አይገባም – ክብር ለነሱ ይሁን።

ኦጋዴን እና አካባቢው “ራሴን አስተዳድራለሁ” ብሎ ስራ መጀመሩ ደስ ያሰኛል እንጂ፤ ማንንም አያስቆጣም። ነገር ግን አሁን ያለው አይነት ጥላቻ፤ የአንድ መጥፎ ነገር አመላካች ነው። ሌላው ኢትዮጵያ ለዚያ አካባቢ ህዝብ የከፈለውን መስዋዕትነት ዋጋ የማንሰጠው ከሆነ፤ በርግጥም ችግር አለ ማለት ነው። አንዳንድ የሱማሌ ኢትዮጵያ ሰዎች ሌላውን ብሄር እንዲህ የሚጠሉት ከሆነ፤ “ምናለበት ታላቂቱ ሶማልያ በገዛችን ኖሮ?” የሚል አንደምታን ይፈጥራል።

በኦጋዴን ወይም በሱማሌ ኢትዮጵያ ውስጥ የብሄር ብሄረሰቦችን ቀን ሲከበር፤ በአካባቢው ያሉትን የኦሮሞ ተወላጆች በማቀፍ በልዩነት ውስጥ አብረው መኖራቸው እንደጥሩ ምሳሌ ማሳየት ይቻል ነበር። በብሄር ብሄረሰቦች በአል ሰበብ… ሌላውን ህዝብ ከመሳደብ ይልቅ፤ ስለመስዋዕትነቱ ማመስግን ምንም ክፋት የለውም። ህዝብን ማመስገን ባንችል እንኳን፤ ምናል አምላካችንን ብናመሰግን? አምላክን በትንሹ ማመስገን ካልቻልን ያለንን ያሳጣናልና ተመስገን ማለትን እንወቅበት።

የማመስገን ነገር ከተነሳ አንድ የስንብት ታሪክ እናውጋ።

እኚህ ሰው… በኢትዮ-ሶማልያ ጦርነት ወቅት የኢትዮጵያ አየር ኃይል አብራሪ ነበሩ። በአየር ላይ ሆነው፤ የሱማሌ ተዋጊ ጀቶች ከፊት እና ከኋላ ሲመጡባቸው፤ በአየር ላይ እየተታኮሱ ቆይተው እሳቸው አቅጣጫቸውን ቀይረው ሲምዘገዘጉ፤ ሁለቱ የሱማሌ የጦር ጀቶች እርስ በርስ እንዲጋጩ አድርገው… ጸጥ አሰኝተዋቸዋል። እኚህ የአየር ኃይል አብራሪ በኋላ ላይ የሚያበሩት ጀት ተመትቶ እሳቸው በፓራሹት ወርደው ህይወታቸው ተረፈ። ሆኖም በሱማሌዎች መማረካቸው አልቀረም። ከሌሎች በሺህ የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን ጋር በሱማሊያ እስር ቤት ለአስራ አንድ ከታሰሩ በኋላ ተፈቱ። በእስር ህይወታቸው ያጋጠማቸውን ነገር ሲያጫውቱን እንዲህ አሉ።

“የታሰርኩት በአንድ ጉድጓድ ውስጥ ነው። እጅ እና እግሬ በካቴና ታስሯል። ከላይ ጣርያው ስለተሸፈነ የጸሃይ ሙቀትን እንጂ ብርሃኗን አይቼ አላውቅም። ወደውጭ የሚያወጡኝ ከጨለመ በኋላ በመሆኑ፤ ቀስ በቀስ የአይኔ ብርሃን ደከመ። እንዳልሞት ያህል ጥቂት ምግብ እና ውሃ ይሰጠኝ ነበር። በዚህ አይነት ለብዙ አመታት ስቆይ አምላኬን አማርሬው አላውቅም። አንድ ቀን ግን አምላኬን አማረርኩት። ‘ለምን እንዲህ ታሰቃየኛለህ?’ ብዬ በአምላኬ ላይ አዘንኩበት። የዚያኑ ቀን የነበርኩበትን እስር ቤት ለመጎብኘት አንድ የሱማሌ ወታደራዊ መኮንን መጣ። መኮንኑ እንደመጣ… እኔ ከጨለማው እስር ቤት እንድወጣ አዘዘ። ከዚያም እጅ እና እግሬ እንደታሰረ እሱ ፊት ቀረብኩ። የሱማሌው መኮንን እጅ እና እግሬ የታሰረበትን ሰንሰለት አይቶ ተቆጣ።”

“እንደዚህ አይነት ከፍተኛ እስረኛ እንዲህ ነው የሚታሰረው?” ብሎ አፈጠጠባቸው። አሳሪ ወታደሮች ግራ በመጋባት ዝም አሉ። እኔም አምላኬ ለቅሶዬን ሰማ። በእጆቼ እና በእግሬ ላይ የታሰረው ሰንሰለት ሊፈታልኝ ነው።” ብዬ ደስ አለኝ።

“የጦር መኮንኑ ቁጣውን ሳይቀንስ ሰንሰለቱን ፍቱ።” አላቸው። ከብዙ አመታት በኋላ ሰንሰለቱ ተፈታልኝ። የሱማሌው መኮንን አሁንም እየተቆጣ… “እንዲህ አይነት ከፍተኛ እስረኛ የሚታሰረው እንደዚህ ነው።” ብሎ… ቀኝ እጄን፣ ከቀኝ እግሬ ጋር፤ ግራ እጄን ደግሞ ከግራ እግሬ ጋር እንዲታሰር አዘዘ፤ እንደትእዛዙም ሆነ። በዚህ አይነቱ አዲስ አስተሳሰር… ቢያንስ ቆሜ እሄድ የነበርኩት ሰው አጎንብሼ ቀረሁ። በፊት እጅና እግር ለየብቻ በታሰሩበት ወቅት እንደልቤ እተኛ ነበር። አሁን ግን ለመተኛትም ተቸገርኩ። በፊት የነበረው አስተሳሰር ናፈቀኝ። ያንን ሁሉ አመት ስታሰር አንድም ቀን አምላኬን አማርሬው የማላውቀው ሰው፤ አሁን እርሜን አንድ ቀን ባማርር የባሰ ነገር መጣብኝ።” በማለት… ሰው ባለው ነገር ማመስገን እንዳለበት አስተምረውናል።

እኚህ በሱማሌ ጦርነት ወቅት ለአገራቸው ትልቅ ውለታ የሰሩ የኢትዮጵያ አየር ኃይል አብራሪ ታደለ ይባላሉ። (የአየር ኃይል ማዕረጋቸውን አላውቀውም) ከ11 አመታት እስር በኋላ ከሱማሊያ እስር ቤት ተፈትተው አገራቸው ከገቡት ኢትዮጵያዊ አንዱ ናቸው። ለ11 አመታት ብርሃን ባለማየታቸው የአይናቸውን ብርሃን ሊያጡ ተቃርበው፤ በህክምና ነገሮች ወደነበሩበት ተመልሰውላቸዋል።

እኚህ አብራሪ ከእስር ቤት ከወጡ በኋላ አንድ ልጅ ወለዱ፤ ስሙንም “በፀጋው” አሉት። ሃያ ምናምን አመታት ተቆጠረ። በፀጋው ታደለ ኢትዮጵያ አድጎ ለትምህርት ወደ አትላንታ መጥቶ፤ በታዋቂው ሞርሃውስ ዩኒቨርስቲ ሲመረቅ፤ ከትምህርት ቤቱ በሙሉ ከፍተኛ ነጥብ በማስመዝገቡ፤ ድንቅ ተማሪ ተብሎ… ሁሉንም ተማሪ በመወከል ንግግር ያደረገው እሱ ነበር። በእለቱ እንግዳ ሆነው የተገኙት የአሜሪካው ፕሬዘዳንት ባራክ ኦባማ ንግግራቸውን ከመጀመራቸው በፊት፤ መምህራኑን አመሰገኑ። ለዚህ ኢትዮጵያዊ ወጣት አድናቆታቸውን ለገሱት።

ስለሱማሌ እስር ቤት አስከፊነት እና ስለጭካኔያቸው አቶ ታደለ ከማንም የበለጠ አደባባይ ወጥተው መናገር ይችላሉ። እሳቸው ግን ያለፈውን እንዳለፈ ትተው፤ አዲስ ህይወት በመጀመራቸው ራሳቸው ተከብረው፤ ሌላውን ኢትዮጵያዊ የሚያስከብር ልጅ ለትውልድ አስረከቡ።

በሌላ በኩል ደግሞ ኦጋዴን ወይም የኢትዮጵያ ሱማሌ ከሽግግር መንግስቱ ግዜ ጀምሮ እስካሁን አስር የክልል ፕሬዘዳንቶች ተፈራርቀውባታል። ከነዚህ ፕሬዘዳንቶች መካከል አንዱ በኢትዮጵያ እና ሶማልያ ጦርነት ወቅት የሶማልያ አየር ኃይል ባልደረባ የነበረና ኢትዮጵያን በአየር ሲደበድብ የነበረ ሰው ነው። አንበሳው የኢትዮጵያ ጦር ተጠናክሮ በመጣበት ወቅት… በፋፈም ሸለቆ በኩል አድርገው ወደ ሃርጌሳ ይሮጡ የነበሩ ሰዎች ዛሬ ወደ ኢትዮጵያ ተመልሰው፤ በብሄር ብሄረሰቦች በአል ሽፋን ሌላውን እየሰደቡት ነው። እንዲህ አይነቱ አሳፋሪ ተግባር የማይደገም ስለመሆኑ ምንም ዋስትና የለንም። እነሱ ሌላውን ደገኛ፣ የመሃል እና የዳር አገር ሰዎች እያሉ የጥላቻ መርዝ ሲነሰንሱ፤ የኛ ጉልበታችን እውነትን መናገር ነው፤ ታሪክን ማስተማር ነው።

በመሆኑም በኦጋዴን ወይም በሱማሌኢትዮጵያ ክልል ውስጥ… ለአንደኛው ብሄር ወይም ለሌላው ሃይማኖት ሳይሉ… ለኢትዮጵያ ድንበር መከበር እና ለህዝቡ አንድነት ብለው የህይወት መስዋዕት ለከፈሉት ጀግኖች ሁሉ ኢትዮጵያዊ አክብሮት አለን። ስለነሱ ክብር… በጨዋ ኢትዮጵያዊነት ራሳችንን ዝቅ እናደርጋለን… እንደየእምነታችንም በህሊናችን እናስታውሳቸዋለን። እናም ክብር እና ማዕረግ ለነሱ ይሁን።

ዛሬም አንደ ጥንቱ ባርነትና የሰው ንግድ

$
0
0

Ethiopians in Saudi
(ተፈራ ድንበሩ)

በሰዎች መካከል በጥቅም ላይ በሚደረግ ግጭት ጦርነት ከተደረገበት ጊዜ አንሥቶ ተሸናፊዎች በባርነት እንደተገዙ የታወቀ ሲሆን ሰውን እንደ ዕቃ የመሸጥ-መለወጥ ሥራ የተጀመረው በአረብ ነጋዴዎች ነበር። “Hugh Thomas” የሚባል መጽሐፍ ፀሐፊ “The Slave Trade and Robin Blackburn’s The Making of the New slavery“ በሚል ርዕስ በጻፈው መጽሐፍ ላይ እንዳስቀመጠው ከመካከለኛው ዘመን ጀምሮ እሰከ 869 (ኢኤአ) አረቦች ሸቀጥ ይዘው ወደ አፍሪካ ሲወስዱ የአፍሪካ መሪዎች በገዛ ሕዝባቸው ሸቀጣቸውን ይለውጧቸው ነበር ብሏል። ከዚህ በታች ከመጽሐፉ በቀጥታ የተጠቀሰውን ይመለከቷል፦
“…it [slave trade] was pioneered by Arabs, its economic mechanism was invented by the Italian and Portuguese, it mostly run by Western Europeans, and it was conducted with the full cooperation of many African kings.” 1
ጎርዶን ሙሬይ ስለባሪያ ንግድ ከሬጂናልድ ኮፕላንድ ሥራ ጋር በማገናዘብ ያጠናቀረውን ጥናት እንደሚከተለው ገልጾታል፦

Read full Story in PDF/በPDF ለማንበብ እዚህ ይጫኑ

አቶ ቡልቻ ደመቅሳ ስለምኒሊክና ስለኢትዮጵያ

$
0
0

ከዶ/ር ካሳሁን በጋሻው

Ato Bulcha

አቶ ቡልቻ ደመቅሳ

Emperor Menelik II s

እምዬ ምኒልክ፡ የጥቁር ሕዝብ ኩራት

የአጼ ምኒሊክን መቶኛ የሙት አመት መከበር ምክንያት በማድረግ በ DW ሬድዮ በተደረገው ጥያቄና መልስ አቶ ቡልቻ ደመቅሳ፣ ዶ/ር ሓይሌ ላሬቦና ዶ/ር ሹመት ሲሳይ (የታሪክ ተመራማሪዎች) ቃለ መጠይቅ ተደርጎ በሚሰጠው መልስ ላይ ስለ አቶ ቡልቻ ደመቅሳ በተናገሩት ላይ አስተያየቴን አቀርባለሁ። አንባቢያንን ቃለመጠይቁን ቢያዳምጡ ጥሩ ነው ባይ ነኝ፤ ሁለቱ የታሪክ ምሁራን ትምህርታዊ ትንተና ይሰጣሉና፡፡

ውሸት ሲደጋገም እውነት ሊመስል ይችላል፤ በተለይም የአገራችንን የኢትዮጵያን ታሪክ ለማያውቁ እውነታው ምን እንደሚመስል መረጃ ለማቅረብ እሞክራለሁ።

አቶ ቡልቻ ኦሮሞ ከባሌ እየተስፋፋ ሲመጣ ልብነ ድንግል እንዳይስፋፋ አቆሙት ይላሉ፡፡ ለምን ይህን ምሳሌ እንዳቀረቡም ግልጽ አይደለም ለሳቸው ትንታኔ የማይመች በመሆኑ፤ ለዛውም በአጼ ልብነ ድንግልና በኦሮሞች መሀከል ስለነበረው ግኑኝነት በከፊል ዶ/ር ሃይሌ ላሬቦ ሊያስረድዋቸው ሞክረዋል፤ ስለመስፋፋቱና እንዲያውም አማራውን እንደገፋው ለአቶ ቡልቻ መረጃ ላቅርብ፡፡

ጥንት ሌላ ስም የነበራቸው በኦሮሞ ከተያዙ ማግስት ስማቸው የተቀየረ፤ ደዋሮ-ጨርጨር፣ ጋፋት-ሆሮ፣ ገራሪያ-ሰላሌ፣ ዳሞት-ወለጋ፣ አበቤ-በቾ፣ ሽምብራ ኩሬ-ሞጆ … (የሃያኛው ክፍለዘመን ኢትዮጵያ ገጽ 50 በጥላሁን ገ/ስላሴ) በቅኝ ተገዛ የሚሉት ኦሮሞ ተጨማሪ ቦታ እንደያዘ እንጂ እንደተወሰደበት አይደለም ታሪኩ የሚመሰክረው፡፡

BULCHADEMEKSAአቶ ባልቻ የኦሮሞን ታሪክ ከደቡብ አፍሪካ ጋር ሊያዛምዱት ይሞክራሉ፤ ኦሮሞም እንደ ደቡብ አፍሪካ ጥቁሮች ኢትዮጵያ ውስጥ ሲረገጥ የኖረ ሕዝብ አድርገው ያቀርቡታል። መፍትሄውንም ሲጠይቁ reconciliation እርቅ ኦሮሞ ይቅርታ ተጠያቂ የተቀረው ይቅርታ ጠያቂ በተለይም የፈረደበት አማራ ለዚህ ወንጀል ትልቁን ድርሻ ይወስዳል፡፡ ባለፉት አስተዳደሮች ስህተቶች አልተሰሩም ብሎ የሚከራከር የለም፤ ጥያቄው እንዴት አብረን ወደፊት መሄድ እንችላለን ነው?

እንደቅኝ ተገዛን የሚሉት ቡልቻ ደመቅሳ አገሪቱን በእርሻ ሚኒስቴርነትና በምክትል ገንዘብ ሚኒስቴርነት አስተዳድረዋል – ቸር ቅኝ ገዢ ነበር የነበራቸው፤ እኛ ቅኝ እየተገዛን ስለሆንን በሚኒስቴርነት ቅኝ ገዢዬን አላገለግልም ብለው አላንገራገሩም፡፡

ኦሮሞ በሲቪሉም ሆነ በወታደራዊው ክንፉ ታላቅ የሚባሉትን ስልጣኖች ይዞ የኖረና ያለ የህብረተሰብ ክፍል ነው፡፡ አገሪቱ ውስጥ ለነበሩትና ላሉትም ደግ ነገሮችም ሆነ ክፉ ነገሮች ተጠያቂነቱ እኩል ነው፡፡ አቶ ቡልቻ ቅኝ ገዢ የሚሉትን የአማራውን ክፍለሀገር ደጃዝማች ክፍሌ ዳዲ ያስተዳድሩት ነበር፡፡ (ምሳሌ የሚያቀርቡበት ደቡብ አፍሪካ የማስተዳደር ቅንጦት ይቅርና ነጭ በሚዝናናበት ቦታ ጥቁር መግባት አይፈቀድለትም ነበር)፡፡

ስለኦሮሞ ባለስልጣናት እስቲ እንመልከት

ምኒሊክ በሸዋ ሲነግሱ የረዷቸው አብሮ አደግ ባልንጀራቸው ጎበና ዳጬ ናቸው፡፡ የወለጋውም አስተዳዳሪ ኩምሳ ምኒሊክን በደጃዝማችነት አግልግለዋል፤ እነ ባልቻ አባ ነፍሶም የማይረሱ ታላቅ ኢትዮጵያውያን ናቸው፡፡

የአጼ ሃይለስላሴ አባት ራስ መኮንን ወልደሚካኤል (ጉዲሳ) አባታቸው ኦሮሞ ነበሩ፤ እናታቸውም ወ/ሮ እመቤት እናታቸው ኦሮሞ ነበሩ፡፡

ራስ ዳርጌ የሸዋው ንጉስ ሳህለስላሴ ከወለዷቸው አራት ወንዶች መሃከል አንዱ ሲሆኑ ጥናታቸው አርሲ ውስጥ የአንድ አካባቢ ኦሮሞ ባላባት ልጅ ነበሩ (አባ ቦራ በታቦር ዋሚ፤ ገጽ 9)

ራስ አበበ አረጋይ መከላከያ ሚኒስትር

አቶ ይልማ ዴሬሳ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር፤ የገንዘብ ሚኒስትር

ደጃዝማች ክፍሌ ዳዲ የጎንደር አስተዳደር

አቶ ቡልቻ ደመቅሳ የእርሻ ሚኒስትርን ምክትል የገንዘብ ሚኒስትር

ሜጀር ጀኔራል ሙሉጌታ ቡሊ የክብር ዘበኛ አዛዥና የባህል ሚኒስትር

ደጀዝማች ገረሱ ዱኪ የኢሊባቡርና የጎሙገፋ አስተዳዳሪ

ሜጀር ጀኔራል ደምሴ ቡልቲ የሁለተኛው ክፍለ ጦር አዛዥ

ሌተና ጀኔራል ጃጌማ ኬሎ የአራተኛው ክፍለጦር አዛዥና የባሌ አስተዳደር

ፊታውራሪ ለማ ወልደጻድቅ የሲዳሞ ምክትል አስተዳደር

ሜ/ጀኔራል አበራ ወልደማርያም የአየር ኃይል ምክትል አዛዥ

ደጃዝማች በቀለ ወያ የጨቦና ጉራጌ አስተዳደር ከዚያም የጨርጨር አስተዳደር

ደጃዝማች ካሳ ወልደማርያም የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንትና የእርሻ ሚኒስትር

አንባቢያን መረዳት ያለብን ሁላችንም በመጀመሪያ ደረጃ ኢትዮጵያውያን መሆናችን ነው፡፡ ሕዝባችን በጋብቻ፣ በእምነት፣ በባሕል፣… የተሳሰረ በመሆኑ መሰረት የሌለው ታሪክ እያነበነቡ ሊበታትኑን የሚያስቡትን ታሪካዊ መረጃ እያቀረብን ወግዱ ልንላቸው ይገባል፡፡ ድር ቢያብር አንበሳ ያስር ነው፤ ምኒሊክም ያስተማሩን መቻቻልን አንድነትንና ፍቅርን ነው፡፡

 

 

በአዲስ አበባ ከ600 በላይ አባዎራዎች ቤታቸውን በ3 ቀናት ውስጥ ለቀው እንዲወጡ ቀጭን ትዕዛዝ ተላለፈ

$
0
0
የአዲስ አበባ ከተማ ገጽታ (ፎቶ ከፋይል)

የአዲስ አበባ ከተማ ገጽታ (ፎቶ ከፋይል)

የኦሮሚያ ክልል ባለስልጣናት ደሃ ገበሬዎችን እያፈናቀሉ ቦታቸውን እየወሰዱ ነው

በአዲስ አበባ ከ600 በላይ አባዎራዎች ቤታቸውን በ3 ቀናት ውስጥ ለቀው እንዲወጡ መታዘዛቸውን ኢሳት ቴሌቭዥን ዘገበ። እንደ ቲቪው ዘገባ ትእዛዙን የሰጠው የቦሌ ክፍለከተማ ሲሆን፣ ነዋሪዎቹ እስከ ማክሰኞ ቤታቸውን ለቀው ካልወጡ ፣ አፍራሽ ግብረሀይል በጉልበት እንደሚያፈርስባቸው አስታውቋል።
“በሶስት ቀናት ውስጥ የት እንሄዳለን?’ ሲሉ የሚጠይቁት ነዋሪዎች ፣በአሁኑ ጊዜ በአዲስ አበባ የሚታየው የቤት ኪራይ መጨመር አስግቶናል ብለዋል። ሜዳ ላይ እንዃ እንዳንወድቅ ሜዳውም እየታረሰ ነው ሲሉ ነዋሪዎች ምሬታቸውን ገልጸዋል ሲል ዘግቧል።

በተያያዘ ዜናም ኢሳት በዜና ዘገባው በኦሮሚያ ልዩ ዞን የሚገኙ ባለስልጣናት በስልጣናቸው ደሀ ገበሬዎችን እያፈናቀሉ ቦታዎቻቸውን እየወሰዱባቸው ነው ሲል ዘገበ። ነዋሪዎችን ጠቅሶ እንደዘገበው አርሶአደሮች በጉልበት መሬታቸውን እየተቀሙ ለበለጠ ድህነት እየተጋለጡ መሆኑን አስታውቋል። ከተቀሙት አርሶ አደሮች መካከል በሰበታ ነዋሪ ከሆኑት አንዱ ሲናገሩ የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ የሆኑት የአቶ ደምሴ ቡላ ባለቤት መሬታቸውን በጉልበት እንደነጠቁዋቸውና ክስ ሲመሰርቱም እንዳሳሰሩዋቸው ተናግረዋል ያለው ኢሳት በአዲስ አበባ በተለያዩ አካባቢዎች ቤት ሰርተው ይኖሩ ነበሩ ሰዎች ቤቶቻቸው ከፈረሱባቸው በሁዋላ ለከፍተኛ ችግር መዳረጋቸው ይታወቃል ሲል የዜና ዘገባውን አጠቃሏል።

በጎተራ አካባቢ አንድ ኩምቢ ቮልስ መኪና በቃጠሎ ቢወድምም የ14 ህፃናት ሕይወት ተርፏል

$
0
0

ከሰላም ገረመው
Gotera fire
(አዲስ አድማስ) 14 ህፃናት ተማሪዎችን አሳፍሮ ከጎተራ ወደ ካቴድራል ትምህርት ቤት ይጓዝ በነበረ ኩምቢ ቮልስ መኪና ላይ ባልታወቀ ምክንያት በተነሳ እሳት ሙሉ በሙሉ የወደመ ሲሆን በህፃናቱ ላይ ምንም አይነት አደጋ አለመድረሱ ታውቋል፡፡ ጎተራ ማሳለጫ ላይ ከመኪናው የፊት አካል የተነሳውን እሳት የተመለከተው ሹፌሩ፤ ልጆቹን ፈጥኖ ከመኪናው በማውጣቱ በህይወት ላይ አደጋ አለመድረሱን የጠቆመው ፖሊስ፤ መኪናው በምን ምክንያት ለእሳት ቃጠሎ እንደተዳረገ የቂርቆስ ፖሊስ መምሪያ ምርመራ እያደረገ መሆኑን አመልክቷል፡፡ እሳቱ በምን እንደተነሳ የተጠየቀው ሹፌሩ፤ እሱም ምክንያቱን እንደማያውቅ ተናግሯል፡፡ ስለ አደጋው ያነጋገርናቸው የእሳትና ድንገተኛ አደጋ የህዝብ ግንኙነት ሃላፊ አቶ ንጋቱ ማሞ በበኩላቸው፤ መኪናው 8 ሰው ብቻ መጫን ያለበት ቢሆንም 14 ህፃናት አሳፍሮ እንደነበር ገልፀዋል፡፡ እሳቱን ለማጥፋት ከ25 ሺህ ሊትር በላይ ፈሳሽ እንደፈጀና መኪናው በቃጠሎው ከጥቅም ውጭ እንደሆነ አቶ ንጋቱ ገልፀዋል፡፡
(ምንጭ አዲስ አድማስ ጋዜጣ አዲስ አበባ)

ኃያሉ አፄ ሚኒሊክ ለሴቶች እኩልነት ተግባራዊነት ዓለምን የቀደሙ ንጉሥ

$
0
0

ከሥርጉተ ሥላሴ 

ስርጉተሥላሴ

ስርጉተሥላሴ

ያን ዘመን ሳስበው ዛሬን መስለችን ያስለቅሰኛል። ያን ፈርጣማ ዘመን ሳስታውሰው ዛሬ ውስጣችነን መሳሳቱ ያቃጥለኛል። ያን ገድላማ ብቁ፣ ሥልጡን፣ ልዑቅ የአመራር ጥብብ ሳናግረው ግን መጽናናትን፣ ሙላትን ያጎናጽፍልኛል። ክብራቻን፤ ማንነታችን፤ ተፈሪነታችን፤ መሪነታችን፤ ብልህነታችን፤ እርግጠኛ ያደረጋል፤ የቀደምቶቹ ብቃት የሰማይ ገደል ለዛሬ ፍንጣቂ ማስተዋል ቢልክልን አምላኬ ምን አለበትም እላለሁ። የባዕዳን ግራሞት ጭብጥ፤ የእርስ በርስ ችግራችውን ዋጥ አድርገው በጋራ ቆመው ትንግርትን ሰማዕታት ማዘከራቸው የህሊናችን ዳኛ ሆኖ እኛን ሊገራን ባለመቻሉ ግን የልቤ ክናድ ይላል። ነገ ሌላ ቀን ነውና ነገን እንዲመርቅልን ህይወቱ ያላቸው አበው ሱባዬ ቢይዙበት ምኞቴና ናፍቆቴ ነው … አንደ ዕምነታቸው።

ዓለም ስለ ሴቶች ብቃት ብጣቂ እውቀት ባልነበረበት ጊዜ የኛው አፄ ኃያሉ ንጉሥ ሚኒሊክ ደማቸው – መንፈሳቸው – ሙሉዕ ፈቃድ ሰጥቶ ተግባር ላይ የዋለ በኽረ ጉዳይ ነበር የሴቶች እኩልነት። ኢትዮጵያ ሚስጢር ናት። ኢትዮጵያ ገድል ናት። ኢትዮጵያ ዓለም – ዓቀፍ ህግ ናት።  ኢትዮጵያ የቀደመች ሥልጡን መምህርት ናት። በዘመኑ የጣሊያን ተጋነት፤  የኢትዮጵያ ጥበበኛው መሪ የአፄ ሚኒሊክ አመራር ደግሞ ዕርቅና ሰላም ፈላጊነት ዓለምን ያሰደመመ መረቅ ትውፊት ነበር። ምርኮኛን ተንከባክቦና መርቶ ወደ ሀገሩ መሸኘትም አብነታዊ የአፄ ሚኒልክ ልዑቅ በኽረ ተግባር ነበር። ዛሬ ያሉት ሰበነካዊ ዓለምዓቀፍ ድርጅቶች መሰረተ ጥንስስ ብቻ ሳይሆን ዓላማው ቀድሞ ኢትዮጵያ መሬት ላይ በድርጊታ ላይ የዋለው በድንቅነሽ አንባ ነበር – በብጡሎቹ።

ሀ. የእኩል ተሳትፎ ፈቃድ … ለሴቶች።

የጣሊያን ከመቀሌ አልፎ መስፋፋትን መመረጡ ያልተማቻቸው ንጉሥ ሚኒሊክ አልጋቸውን ለአጎታቸው ለራስ ዳርጌ አደራ ሰጥተው፤ ረዳትም ደጃዝማች ኃይለማርያምንና የወህኒ አዛዡን ወልደ ጻድቅን ጨምረው ሊነሱ ሲያስቡ ባለቤታቸው እቴጌ ጣይቱ አልለይም ሲሉ ሙሉ እምነትና ፈቃድ ሰጡና እቴጌ ጣይቱ አብረው ዘመቱ። „ … ከጃንሆይ ጋር እቴጌ ጣይቱ አልለይም ብለው ጦራቸውን ይዘው ተጓዙ“ (ገጽ 100*)  „ „ወንድ ያለ ዕለት – በዕለት፤ ሴት ባለ በዓመት“ የሚለውን የሴቶችን መብት ደፍጣጭና ተጫኝ ኮስሳ ብሂል ቅስሙን እንኩት አድርገው የአካላቸውን ክፋይ የማይገሰስ ክብር ሰጥተው፤ ፈቃዳቸውንም ተንከባባክበውና አልምተው የታሪክ ዐይነታ ታዳሚ አደረጉት። ዘመናቸውንም ሙሉና ጌጣማ አደረጉት። የቀደመና የሰለጠነ መክሊት ባላጸጋው የንጉሦች ንጉሥ አፄ ሚኒሊክ የተግባር ምሰሶና ዋልታ ነበሩ ለሁለመናችን።

minilikለ. የጦር ጄኒራልነት፣ የአዋጊነት፣ የመሪነት፣ የአዝማችነት ጥንድ የእኩልነት ዕውቅና እና ዕሴቱ – ለሴቶች።

 ዓለምዓቀፉ የቅኝ ግዛትን ቅስም የሰበሩት ክቡር አፄ ሚኒሊክ „ሴትና አህያ በዱላ“ የሚለውንም ሥነ – ቃል ጨፍልቀው ከጠላት ጋር ለጦርነት ዐዲማህለያ ላይ በ10 ግንባር ካሰለፉት 30 ሺህ ጦር ውስጥ የልዕልታችን፤ የንግሥታችን  የእመቤት ጣይቱ ግንባር ከ3ሺህ ጦር ጋር አንዱ ግንባር ነበር። ይህ በዬትኛው የዓለም ታሪክና መዘክር የሚገኝ ጣዝማዊ ገቢር ነው። ማንም ሀገር እንዲህ በዚያ ዘመን የተግባር ዲታ የሆነ የሴቶች የእኩልነት ታሪክ የለውም። አባታችን፤ መሪያችን፤ መኩሪያችንና ንጉሣችን አፄ ሚኒሊክ ግን እኩልነትን የተቀበለ፤ እኩልነት በድርጊት ያዋለ፤ እኩልነትን ያከበረ – ያስከበረ – ያደመጠ፤ እኩልነትን በጥንግ ድርብ ካባ ያንቆጠቆጠ የመኖራችን ልዩ የታሪክ ጉልላት እንዲያብብ ፈቀዱ።

ስለዚህ አፄ ሚኒሊክ ለእኛ ለኢትዮጵያ ሴቶች ብቻም ሳይሆን ዓለምን በድርጊት ያስተማሩ ድንቅ የኢትዮጵያዊነት አንዱ ታላቅ ሚስጢር ናቸው። ንጉሥ ሚኒሊክ ለሴቶች እንደ አደራጅነተቻው የክብር አባላችን ሰንደቃችን ናቸው።

ኃያሉ የአፍሪካ ቀንዲል ንጉሥ ሚኒሊክ የሴቶችን የብቃት ሚስጢር መንፈስ ቅዱስ ስላቀበላቸው ውጤቱ አዲስ የጥቁር  የማይደፈር የድል ፕላኔት ሆነ። በውጊያውም ሳይደክሙ እቴጌ ጣይቱ ከአካላቸው ጎን ሆኑ በፋመው ውጊያ ላይ “ …  በዚህ ጊዜ ዐፄ ሚኒሊክ የጦር ወታደራቸውን በሚያበራታታ ቃል ሲያደፋፍሩ፤ እንዲሁም እቴጌ ጣይቱ እንደ ወንድ በጦርነቱ መካካል እዬተላላፉ የቆሰለውን ሲያነሱ፤ ለተጠማው መጠጥ፤ ለተራበው ምግብ ሲሰጡ ዋሉ“* ይሉናል ሊቁ ጸሐፊ (ገጽ 110 )የተደራጀ የቀይ መስቀል ተግባር በእናትነት ተፈጥሯዊ ክህሎት በቅሎ፤ በአጋርነት ጸድቆ፤ እንሆ … ሚስጢር ይቀዳል ከድንቅነሽ አንባ …. ከእግዚአብሄር በታች እኩልነታችን ያፀደቁ ብቸኛ መሪ፤ የእኩልነታችን መሸሸጊያ የልብ አድርስ እረኛ ፤ አስተዋሽ ጌታ ንጉሥ ሙሴ አፄ ሚኒሊክ።

ሐ. የእቴጌ ጣይቱ ብርሃነ ዘ ኢትዮጵያ በፖለቲካ እኩል የመወሰን አቀም ይለፍ በሀሴት ያረገበት ዕውነት፤

  “ሴት ቢያውቅ በወንድ ያልቅ“ ተረት ሆኖ ቀራንዮ የዋለበት ሌላው ትርጉም እቴጌ በባለቤታቸው የነበራቸው የላቀ ተደማጭነትና ተቀባይነት ነበር። ሴትነት ሰማይ ያረገበት ልበለው ከቶ? የአማካሪነት ልዩ ፈቃድ በገፍ ማግኘትና የመደመጥ እርግጠኝነት በልበ ሙሉነት መለገስ … አፄ ሚኒሊክ ለእቴጌ ጣይቱ ወደው ሰጡ። በጠባያቸው፣ በብልህነታቸው፣ በጣም ይወዷቸውና ያከብሯቸው ስለነበረ አብዛኛውን ጊዜ ውሳኔው የሚፀናው በእቴጌ ጣይቴ እንደ ነበረ ሊቁ ተክለጻድቅ መኩሪያ እንዲህ ይገልጡታል“ … አቴጌ የጠሉት ይነቀፋል ከሹመትም ይሻራል፤ የወደዱትም በንጉሰ ነገሠቱ ዘንድ ክብርና ሹመትም ያገኛል። ስለዚህ መሳፍንቱንና መኳንነቱ ንጉሡ ነገሥቱን እንደሚፈሩና ደጅ እንደሚጠኑ ሁሉ እንዲሁም እቴጌዪቱንም ደጅ ይጠኑ ነበር።  ዋው! ቅቤ የሚያጠጣ አንጀት የሚያረሰርስ ተመክሮ ነው። እንዴት ድንቅ ፈለፈል የሆነ ውብ ጥልፋማ ዘመን ነበር።

„ሴትና አይህያ … „ ቀርቶ … ውሳኔ የማመንጨት፤ የማሻሻል፤ የመሰረዝ የብቃት ልኬታን ይለፍ የሰጠው፤ እንዲሁም  የእቴጌ በራስ የመተማማን ስኬታማ ጉዞ  … ሲፈተሽ ደግሞ  „ይልቁንም የውጫሌ ውል የ17ኛው አንቀጽ ንግግር እንዲለወጥ በዐፄ ሚኒሊክና በኮንቱ አንቶኔሊ መካካል ክርክር ሲደረግ እቴጌይቱ በክርክሩ እዬገቡ ይነጋገሩበት ነበር። በኋለም በ 17ኘው አንቀጽ ንግግር ፈንታ የኢትዮጵያ ንጉሠ – ነገሥት ከመሬቱ አንድ ክፍል ወይንም በ17ኛው አንቀጽ የተባለውን ጥገኝነት ለሌላ ለውጭ አገር መንግሥት እንዳይሰጥ  ግዴታ ይግባና ይለወጥ ብሎ ሲያቀርብ …  ንጉሠ ነገሥቱ ይህንን ሃሳብ ከራስ መኮነን ጋር ሲመካካሩ እቴጌይቱ የፈቀድነውን ብናደርግ የኛ የግል ሥልጣናችን ነው እንጂ እሱን በፍጹም የሚያገባው ነገር የለም ብለው ውሉ እንዲቀር አደረጉ“ (ገጽ 131 እና 132)*

Emperor Menelik II sይህን ያህል ክብራችን ንጉሥ ሚኒሊክ ፍጹም የሆነ ሙሉ እምነት በሴቶች ብቃትና የመወሰን አቅም ነበራቸው። የሴቶችን ማንም ሊጋረው የማይችለውን የእናትነት ሰማያዊ ጸጋ ሥራ ላይ የዋሉ ብቸኛ ንጉሥ። ስለሆነም ሀገራቸውን፤ ሰንደቃቸውን ዳር ደንባራቸውን አስከበረው ተከበሩ። ምክር ስለ አዳመጡ ፍላጎታቸውን እውን አድርገው በሥልጣኔ ጎዳና እናት ኢትዮጵያን መሩ። ነፃነታችን በድል ስላቀለሙት አንገታችን ደፍተን ከመኖር ታደጉን። ተፈሪ፤ በራስ ቋንቋ የምትናገር፤ በቅኝ ያልተገዛች ብቸኛ አፍሪካዊት ሀገር፤ በራሷ ፊደል የምትጽፍ ሀገር፤ የጥቁር መመኪያና መጠጊያ፤ የእኔ የምትለው ህግ – ባህል – ወግ – እምነትና ልማድ ያላት ውብ ሀገር በደማቸው ሸለሙን። ቅይጥና የትውስት ነገር አልነበረንም። ሁለመናችን ጠረኑ እኛን ይመስል ነበር። የዛሬን አያድርገው አረሙ ወያኔ ለባዕድ እስከ ሸጠው እስከለወጠው ዱድማ ዘመን ድረስ ….። ክብራችን እናመሰግነዎታለን። ጌታችን እንወደወታለን ጸሐያችን፤  እመቤታችን ብርሃነ ዘ ኢትዮጵያ …. እቴጌ ጣይቱም የድርጊት ጀግንነተወት የተስፋችን ማህደር ነውና እናፈቅረወታለን። አላሰፈሩንም። ይልቁንም ድፈርትን አዋጡን እንጂ ….

ይቋጭ መሰል … ደግመን ያለገኘው እድል ነው ኃያሉ ሚኒሊክ በዛ ዘመን ሰጥተውን የነበረው። የእኩልነት ዕውቅና፤ የመኖር ነፃነት ኪናዊ ቃና። አፄ ሚኒሊክ ለሴቶች ተቀድቶ የማያልቅ ባለውለታ፣ ክንድና ደጅን ነበሩ።ይህ ዝቀሽ ታሪክ የሀገርን ዳር ደንበር በማስከበር ብቻ የተወሰነ አልነበረም። ለሰው ልጆች መብት ማስከበሪያ የዲሞክራሲ ሂደት ልዕል ጉልትም ነው ትምሀርት ቤት።

በዘመኑ በነበሩ ሌሎች መንግሥታዊ አስተዳደሮችና መዋቅሮች አመሰራረት ሆነ አመራር፤ እንዲሁም በኢትዮጵያ የሥልጣኔ ጉዞ እርምጃ በተሰጣቸው የእኩልነት መብት እቴጌ ጣይቱ መጠነ ሰፊ ተግባራትን በመከወን የሴቶች ኮከብ፤ እመ ብዙኃን መሆን ችለዋል። ስለሆነም እቴጌ የናሙና የተግባር ተቋም ነበሩ። ያገኙትም ዕድል ባክኖ አልቀረም።  በአግባቡ በብልህነት ተጠቅመው ጸጋቸውን ዓለም እራሱ እንዲመሰክርበት አድርገዋል። የሰከነው ተሳትፏቸው በተግባር ከብሮ ሀገርን ያህል ዕንቁ ነገር አተረፈ። ትውልድን ገነባ። በነገራችን ላይ የቀደመው የእናት ሀገራችን ምስላዊ ካርታ እኮ እንደ ሌሎች ሀገሮች ቅኝ ለማደረግ ባሰበት ተሰመሮ የተሰጠን አልነበረም። በፍጹም! በደምና በአጥንት የጸደቀ አልማዝ እንጂ …. ። ይህ አዲሱ ዜማ „ጣይቱ የኛቱ“ ትንቢት ዕውን ከሆነ ኢትዮጵያዊነት እንደ ገና ያበራል። ተስፋ አያልቅ … ም። በመጨረሻ — አብሮነት ደስ ይላል – ያሳምራል … በመንፈስ ሃዲድ ለነበረን ቆይታ ትህትና ከአክበሮታዊ ምስጋና ጋር ሸለምኳችሁ።

ማሳሰቢያ  በትምህርተ ጥቅስ ባሉት ሥንኞች ውስጥ በጉልህ የተጻፉትና የተሰመረባቸው ኃይለ ቃላት፤ የበለጠ ለማሰረገጥ ብዬ እኔ እንጂ መጸሐፉ ላይ የለውም። በትምህርተ ጥቅስ ውስጥ የሚገኙት ኮከብ ያለባቸው አገላለፆች ሁሉ ገፃቸው ከላይ ተጽፏል፤ የደራሲው ሥምና የመጸሐፉ እርእስ ሲደጋጋም እንዳትሰለቹ በማለት ከላይ አልጻፍኩትም።

( በ1936 ዓ.ም የኢትዮጵያ ታሪክ – ከዐፄ ቴወድሮስ እስከ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ከሊቀ ሊቃውነቱ ክቡር ተክለ ጻድቅ መኩሪያ መጸሐፍ የተወሰደ ነው) ከትህትና ጋር ..

ኢትዮጵያና ኢትዮጵያዊነት ለዘለዓለም ያዘራሉ!

እግዚአብሄር ይስጥልኝ::

ይቁረጥ –በዳዊት ዳባ

$
0
0

ዳዊት ዳባ
Friday, December 06, 2013
denfo.dd46.gmail.com

1998 በቅድስት ባይልልኝ ተደርሶና  ተዘጋጅቶ ለእይታ የቀረበው ህይወት እንደዋዛ ድራማ ላእይታ ከቀረበ ሀያ አንድ አመት ሆነው። ቅድስት በዚህ ስራዋ በየአረብ አገሩ ለስራ የሚላኩ ዜጎች በይበልጥም የሴት እህቶቻችን ሂወት ምን ያህል በመከራና ስቃይ የተሞላ እንደሆነ እንደወረደና መታየት በሚገባው መንግድ አሳይታናለች። ይህንን ፊልም በጊዜው ሁላችንም ተመልክተን ጉድ ብለናል። ለረጅም ጊዜ ዋና መወያያችንም ነበር።  መንግስት ነን ያሉት ለቀጣይ ሀያ ምናምን አመታት በየአረብ አገራቱ ወንድምና እህቶቻችንን በገፍ ሲልኩ በነዚህ አገራት የሚጠብቃቸውን ፍዳ አናውቅም ነበር ሊሉ አይችሉም። ይህ ፊልም የችግሩን መነሻ ጊዜ አመላካችም ነው።

በቀጠሉት አመታት በመከራ ብዛት አይምሯቸው ታውኮ ወይ ያካል ጉዳተኛ ሆነው ያለረፍት ከመስራትና በተለያዩ መንገዶች ክብር የሆነ ሂወታቸውን አጥተው   እሬሳቸው ወደ አገር  የተመለሱ ወገኖቻችን ከመብዛታቸው ብዛት አሁን አሁን በትናንሿ መንደር ደረጃ ብዙም ማሰብ ሳይፈልግ ሁሉም ዜጋ በስም እየጠራ በቁጥር የሚያስቀምጠው ሆኗል። እረ እንደውም በዘምድ አዝማድ መሀል። አንድ ወይ ከዛም በላይ ሉሁላችንም ተዳርሷል።  እንትና እኮ አረብ ሀገር ሄዳ ከዛ ያሳዝናል ብለን የምናወራው አንጀት የሚያኮማትር ሀዘናችን ከሆነ ውሎ አደረ ። ዛሬ የእንባሲ ሰዎቻችው አይምሯቸው ታውኮና ለዘላለሙ እንዳይድኑ በሽተኛ ሆነው የሚመለሱትን ሳይጨምሩ በሳምንት ከስድስት እስከአስር እሬሳ ወደ አገር እንልክ ነበር እያሉን ነው። በእርግጥ ይህን መነገርም አያሻንም እናውቅ ነበር።

ከአገር ቤት ወደ አደጉት አገራት የሚበሩ አይሮፕላኖች የኛዎቹን ጨምሮ በማደጎ ስም የሚቸበቸቡ ኢትዬጵያዊ ህጻናት ወና ደንበኞቻቸው ናቸው።  በተመሳሳይ ጦርነት ላይ ያለች አገር እስክትመስል ከየአረቡ አገራት ወደ ኢትዮጵያ የሚደረጉ በረራዎች እሬሳና ህሙማምን  በገፍ ማመላለስ ከጀመሩ ሀያዎቹን አመታት አስቆጥረዋል። በየአረብ አገራቱ ተጎጂ ስለሆኑ ዜጎቻችን ስናወራ የምናወራው ስለ አምስት ሞቶ ሺ ተጎጂዎች ወይ ስለ አንድ ሚሎዮን ተጎጂ ዜጎች አይደለም። ስለ ብዙ ሚሊዮን ተጎጂ ዜጎች ነው?። በተመሳሳይ  የምናወራው ዛሬ ሳውዲ አረቢያ ውስጥ እየሆነ ስላለው ብቻ አይደለም ሀያ ሶስት አመት ስላስቆጠረ የዜጎቻችን መከራና አገራዊ ችግር ነው።

እነዚህ ብዙ ሚሊዮን ሰቆቃ የተፈፀመባቸው ዜጎች የበዙት ህጋዊ በሚባለው መንገድ ወደየ አረብ አገራቱ የተላኩ ናቸው። ህጋዊ የሚባለው መንገድ የትኞቹንም ተጎጂዎች እስከዛሬ አልታደገም። ህጋዊ መሆን አለመሆን  ምንም አይነት ልዩነትም አልነበረውም።  ልዩነቱ ፍዳውን ጉዞ ላይ መጀመር ወይ በሚመች አይሮፕላን ቶሎ ቦታው ደርሶ  የመከራውን ሂወት መጀመር ብቻ ነው። ወገኖቻችን እዛ ሲደርሱ ህጋዊ የሚያሰኛቸው ወረቀታቸው ባሰሪዎቻቸው እጅ ስለሚሆን ህገወጥ ብቻ ሳይሆን ያሰሪዎቻቸው ባርያ ነበር የሚሆኑት።  ላለመገደል፤ ላለመደፈር ሰቆቃ እንዳይፈፀምባቸው፤ ጉልበታቸው ያለአግባብ እንዳይበዘበዝ፤ የለፉበትን ሀቃቸውን እንዲይከለከሉ ህጋዊ ወረቀቱም ሆነ ወያኔዎች ተዋዋልን ወይ ስምምነት አደረግን ሲሉት የነበረው ቅራቅንቦ ምንም አልፈየደም።

ይህንን መካድም አይቻልም። አለም ሁሉ ያየውን ያለማቀፋ ሜድያዎችን ሽፋን ካገኙት ውስጥ የጋዳፊ ልጅ ሚስት ወ/ሮ ሀኒባል እህታችን ሸዋዬ ሞላ ላይ ያን ሁሉ ሰቆቃ የፈፀመችባት  ወረቀት ስለሌላት አይደለም። ወይስ ቤሩት ውስጥ ባደባባይ እየደበደቡና ኡ ኡ አድኑኝ፤ የወገን ያለህ እያለች አፍነው የወሰዷትና ጩህቷን አለም ስላየው ወስደው ከገደሏት በሗላ እሯሳን ገደለች ብለው የተፈፀማባትን ግፍ ያዳፈኑት አለም ደቻሳስ እሷም ህገወጥ ስደተኛ ስለነበረች ነበር ወይ?። በጭራሽ። እንዲሁ በየበረሀው የሰውነት ክፍሎቻቸውን የተሰረቁት ወገኖቻችን ህገ ወጥ ስለሆኑ ወይስ ተቆርቋሪ ስለሌላቸውና ውድ የሆነ የሰውነት ክፍላቸውን ስለተፈለገ።

አለም ባልሰለጠነበት ዘመን ሰዎች ያለፍላጎታቸው ባርያ ተደርገው ያድሩ ነበር። እጅግ ዘግናኝ ኢሰባዊ ድርጊት ይፈፀምባቸው እንደነበር አውቃለው። በጊዜው ባሮቹ ሲሸጡ ዋጋ ስላላቸውም ይሆናል  ዋና አላማው በሂወት እንዲኖሩና ስራ በነፃ እንዲሰሩ ነበር። ወያኔዎች  በየአረብ አገራቱ የምትልኳቸው ወገኖቼ ጉዳይ የሚመስለው “እስኪያብዱ ወይ እስኪሞቱ ባሰኛችሁ መንገድ አሟጣችሁ ተጠቀሙባቸው ነው።  ሰቆቃ ፈፅሙባቸው ነው። ሌላ ሙሉ ጉልበት ያለው ይላካል ትቀይሯቸዋላችሁ ነው።”   ይህን እንድል ያደረገኝ በየትኛውም ባርያ ማሳደር ህጋዊ በነበረበት ዘመን  ወይ በየትኛው የባርያ ስርአት የነበረበት አገር  ባርያ የተደረጉ የሰው ልጆች ሰቆቃና ስቃይ ስጋቸው መቋቋም እያቃተው በዚህ ብዛት(ሬሾ) ይሞቱ እንደነበር ወይ  ሰቆቃውን መሸከም እያቃተቸው ያብዱ እንደነበር ስለማላውቅ ነው። “ምን እያደረጓቸው ነው?” “ምን አይነት ማሰቃያ ነው የሚጠቀሙት?” የሚለው ጥያቄ ሁሌም የብዙ ተቆረቀቋሪ  ዜጎችና የኔም መልስ ያላገኘ እንቆቅልሽ ከሆነ ከረመ።

የሚያሳዝነው ግን የበዛው ኢትዮጵያዊ ሀዘኑና መጠቃቱ በየቤቱ እየገባ እያለም ባገር የመጣ(አገራዊ ችግር) አድርጎ በቶሎ አላየውም።  ችግር የሆነው በአገሪቷ ውስጥ ባለው አፈና ግዙፍነት  (አፈናውን በጭራሽ በጭራሽ አሳንሰን አንዳናየው)    ተጎጂዎቹ የሱ እህት፤ የነሱ ሰፈር ልጅ፤ ያአክስቷ ልጅ እንደሆነች እንጂ በብዙ ሚሊዮን የሚቆጠሩ ዜጎች በተመሳሳይ ስለባ እየሆኑ ያሉበት ስር የሰደደ አገራዊ ችግር አድርጎ አለማየቱ ነው።

ሁለተኛው ምክንያት ወደየአረብ አገራቱ የተገፉው ህዝብ በብዙ ሚሊዮኖች የሚቆጠር ነው። ስለ አረብ አገራት ስናወራ የምናወራው ስለህዝብ ነው። ክፉ ሰዎች ያሉትን ያህል ደግና ጥሩ ሰዎች ደግሞ አሉበት። በአገሮቹ መሀከልም የሰማይና የምድር ያህል ልዩነትም አለ። እድለኛ ሆነው እነዚህ ደጋጎች ጋር ተቀጥረው መስራት የቻሉት ወይ ሰቆቃ የማይበዛበት  አገራት ውስጥ የሄዱት ጉዳተኛ የመሆን እድላቸው ያነሰ ስለሆነ የተወሰኑት አምሮባቸው ገንዘብም ይዘው ወደአገር ቤት ይመጣሉ። ጎጆ ይቀይሳሉ፤ ቆርቆሮም ይቀይራሉ። ህዝብ ይህንንም አይቷል ሰምቷልም ስለዚህም ይህንንም አዳምሮ ነው ችግሩን ሲያይ የነበረው።

ሶስተኛው ምክንያት ሰቆቃውን መሸከም አቅቷት እስከመጨረሻው ያንቀላፋችው  ወይ አይምሮውን የሳተውን ጨምር ሁሉም በሂወት እስከነበሩና እስከቻሉበት ጊዜ የገኟትን ወደቤተሰቦቻቸው መወርወራቸውን አላቆሙም። ብዙዎቹ በደም፤ በላባቸው፤ በሰውነታችውና በሂወታቸው ዋጋ ይከፍሉ ነበር እንጂ አኗኗራቸው የገንዘብ ወጪ አልነበረበትም። እጃቸው የገባችውን ሁሉ ነው ሲልኩ የነበሩት። መንግስትን ያፀናው የበዛው ከውጪ ይገባል የሚባለው ገንዘብ በዚህ መንገድ ወደ ወደ አገር ሲፈስ የነበረ ነው። በተጨማሪ መናገር ምንም ላይፈይዱ ቤተሰብ ማሳሰብ ነው ብሎ በደላቸውን መደበቅም አለበት። ድቅድቅ ባለ አፈና ውስጥ ለምንኖር ህዝቦች በነዚህና ይህን በመሰሉ ሊሎች ምክንያቶች ተጨማምረውበት ህዝብ የችግሩን ስፋት፤ የጉዳቱን ደረጃና አገራዊ ውርደት መሆኑን ለማወቅ ጊዜ ቢወስድበት አያስገርምም።

በአግባቡ ያልተረዳነው ግን የችግሩን ደረጃና ስፋት ብቻም አልነበረም ። ከዛሬ ሀያ ሁለት አመት በፊት የመጀመርያዋ አይምሮ ህመምተኛ፤ የመጀመርያው እሬሳ  ሲገባ ጀምሮ መንግስት ያውቅ  እንደነበረም ነው።  የምናወራው የውስጥ ሱሪያችንን ቀለም ለማወቅ ስለሚሰሩ ዘረኛ ውላጆች ነው። በአሀዝ ማስቀመጥ በሚችሉበት ደረጃ አንድ ብሎ ሲጀምር ጀምሮ ያውቁ ነበር ። እኛ ግን ችግሩን በየግሉ ወስደን የልጆቻችን እሬሳ ሲልኩልን ተቀብለን አልቅሰን እንቀብራለን። አብደው ሲመጡ ዜጋው ተቀብሎ በግሉ ለማዳን መከራውን ያያል።

ሌላው አይደለም የበዛው ህዝብ ስር የሰደደ ችግር መሆኑን የሚያውቀውና ተቆርቋሪነቱን ሲያሳይ የነበረውም ወገን ውስጥም ብዙ ቁጥር ያለው  ዋና መሆን ይገባው የነበረውን መንግስት ተብዬው እዚህ አገራዊ ውርደት ውስጥ ያለውን ድርሻና ሀላፊነት  አውጥቶ ነው ችግሩን ሲያይ የነበረው። ዛሬም ድረስ ይህ ዳተኛ አመለካከት አለ።  ዛሬም በሳውዲ በወገኖቹ ላይ እየተፈፀመ ያለውን ሰቆቃ እያየም ይሄ ፖለቲካ  አይደለም  ወይ መንግስትን አታስገቡበት የሚሉ ተላላዎች ብዙ ናቸው። ይህንን አይነት አመለካከት ህዝብ ውስጥ እንዲቀጥል የስራ ድርሻቸው የሆኑ ጊንጦችም አሉ። ወዲያም አደረግነው ወዲህ ግን መሪዎቻችን ዘረኛ ውላጅ ወያኔዎች ባይሆኑ ኖሮ ዛሬ በሳውዲዎች ወገኖቻችን ላይ የተሰራው ወንጀል አይፈፀምም ነበር። ሲጀመር ተቆርቋሪ መንግስት ባለበት፤ ለዛውም ሀያ ሶስት አመት መግዛት የቻለና መንግስቱን ያፀና መንግስት ባለበት አገር ዜጎቹ እራሳቸውን እዚህ አይነት ችግር ውስጥ ማግኘት አልነበረባቸውም። አንዴ ከገቡም ዘረኛ ውላጅ ወያኔዎች ባይሆኑ ስልጣን ላይ ያሉት በጣም፤ በጣም፤ በጣም በቀላሉ ይህን ግፍና ውርደት ማስቀረት ይቻል ነበር። ሰውዲ አረቢያ ውስጥ የሆነው በቀላሉ በርግጠኛነት  መከላከል ይቻል የነበረ ችግር ነው። የሰማነው አይነት ዎይታ በሌለበትና በሰከነ ሁኔታ በቀላሉ ወደ አገራቸው መመለስ ሲቻል ነው እነዚህ ጉዶች ቁጭ ብለው ሲያዩ የከረሙት። ዛሬ  የህዝብ ጩህትና ውግዘቱ ሲበዛ ተንደፋድፈውና አተረማምሰውት ይባስ ብለው ችግሩን ፎቶ መነሻና መታያ አድርገው ከውነውታል።

“ይቁረጥ!። ማንሿከክ አላውቅ ወይ በተፈጥሮዬ ማሽንክነት የለብኝም። ይቁረጥ ብያለው። ያለበለዚያ እኔ እቆርጥልሀለው”። ከረጅም ጊዜ በፊት ካየሁት ድራማ ሁሌም የማስታውሰው ትወና ነው።

ዛሬ በአለም ያሉ የደሀ ይሁን የሀብታም፤ አንባገነናዊ ይሁኑ ዲሞክራሲያዊ፤ አፍሪካዊ ይሁኑ ኢሲያዊ፤ ትናንት ነፃ የወጡም ይሁን የኛ አይነት የጠገበ ታሪክ ያላቸው አገራት የየትኛዎቹም አይነት መንግስታት ህዝበቸው በሌላ አገር መንግስታትና ህዝብ በዚህ ደረጃ ሰቆቃ እንዲፈፀምበት አይፈቅዱም። ሲፈፅም ማየትም የሚያስደስታቸው አይደሉም። ለሀያ ሶስት አመት አይደለም ለአንድ ቀንም የዜጎቻቸውን ያለ አግባብ መበደል አይተው ዝም የሚሉም በጭራሽ አንዳቸውም አይደሉም። በአሁኑ ጊዜ በአለም ላይ ያሉ መንግስታት በሙሉ የሚመሩት ህዝብ እራሱን የዚህ አይነት ችግር ውስጥ እንዳይገባ ያቅማቸውን የሚቻላቸውን ሁሉ የሚያደርጉ  ናቸው። ለማድረግ ቁርጠኛነቱና ፍላጎቱም ያላቸው ናቸው። ስለዚህም ይቁረጥ ብያለው።

ዛሬ በኛ ላይ እየሆነ ያለው ወገንታዊ የሆነ መንግስት ስለሌን ብቻ ነው። የምንሰማውን የወገን መገደል፤ መደፈር፤ ይውጡልን መባል መንጓጠጥ፤ ማበድ በአጠቃላይ በየአረብ አገራቱ በወገናችን ላይ የደረሰውን ሰቆቃ ሁሉ  ማስቀረት የሚቻልበት አንድ ሚሊዮን ቀላል የሆኑ መንገዶች ባሉበት የሚፈፅም ነው። ምን ያደርጋል የኛዎቹ መሪዎች ጋር ፍላጎቱ የለማ። ወገንታዊነት ሸቀጥ አይደለም። እሱቅ የማይሸጥ ሆነ። ስለዚህም ለምን? እኛ ኢትዮጵያዊያን ላይ ብሎ ለሚጠይቅ በቂ ከበቂ በላይ አጥጋቢ የሆነ ምክንያት ያለው ችግር ነው። ወደፊትም የሚገዙን ወያኔዎች እስከሆኑ የዚህ አይነት አገራዊ ውርደትና የዜጎች መጎዳት የሚቀጥል ነው።

ችግሩ ላይ የዜጎች ግንዛቤና’ የመንግስት አያያዝ እላይ ባየንበት ጠቅለል ያለ ሁኔታ ላይ እያለ ነው ኢሳት አገልግሎቱን የጀመረው። ኢሳት በዋናነት ህዝብን ስለችግሩ በማሳወቅ ከፍ ያለ ሚና ተጫውቷል። ላለፉት ሶስት አመት ተኩል ህዝብ ማወቅ መብቱ የሆነውን እውነት ይነግረው ጀመረ። የመንግሰት ደርሻ፤ ግዴለሽነትና ዜጎቹን ለመታደግ አለመፈለግ ያጋለጥ ገባ።  ወያኔዎች አያሳደዱና እያዋከቡ እነዚህ የመከራ አገር የከተታቸው ጋዜጠኞች እቦታው ሆነው የመከራውን ብዛት እውነቱን የማጋለጥ የጀግና ስራቸውን ቀጠሉበት፤ ወገንታዊ ሜዲያዎች ይህ የዜጎች ሰቆቃና መከራ ዋና አምዳቸው ሆነ። ምሁራን ፀሀፍት እንዲሁ በውጪም በአገር ውስጥም ያሉ የፖለቲካ ድርጅቶችና ወገንታዊ የሆኑ ዜጎች ባገኙት አጋጣሚ ይናገሩበት ይፅፉበት ጀመረ። ችግሩ ሊደበቅ ከሚችለው ደረጃ አልፎ የውጪ ሜዲያዎች ሽፋን ማግኘት ጀመረ። እንደምናያው ተንተክትኮ ተንተክትኮ መገንፈል ጀመራል። እዚህ ላይ ያለማቀፉ የሴቶች ማህበር ያደረገው ያላሰለሰ ጥረት  እጅጉኑ የሚያስመሰግናቸው ነው።

ወያኔዎች ይህን አገራዊ ውርደት የችግሩን መጠንና የተጎጂ ዜጎችን ሰቆቃ ግዝፈትና በነሱ ምክንያት ይህ መከራ አንደመጣብን ህዝቡ ማወቁ እየጨመረ መሄዱን ሲገነዘቡ ሳይቃጠል በቅጠል እንዲሉ በሟቹ መለስ ዜናዊ የተደረሰ ‘ያዞ እንባ” የተሰኘ ድራማ መፍትሄ ነው ብለው መተወን ጀመሩ። ከሀያ ሁለት አመት በሗላ  መሆኑ ነው።ክንቅልፍ እንደባነነ ህፃን በገፍ ለመካራ ሂወት ስላጋዟችውና ስላሰደዷቸው ዜጎቻችን እንደማያውቁ ሆነው እንደ አዲስ ሊነግሩን ጀመሩ።  መፍትሄ ፈላጊዎች ችግሩ ላይ ተረቃቂዎች ሆነው ለመታየ እላይ እታች አሉ። ተሰብስበው አልቅሰው ሊያስምኑን ሁሉ ሞክረዋል። ይህ መራወጥ የገባው ድራማውን “ከአዞ እንባ” ወድ “ሀይሌ እንባ”  ቀይሮ ቁጭ ብሎ አየው።   መፍትሄ ብለው የሞከሩት ድራማ ያስገኘው ውጤት ህዝብ የበለጠ ስለችግሩ እንዲያውቅና መታየት በሚገባው መንገድ የገዘፈ ሀገራዊ ችግር አድርጎ እንዲያየው ማድረግ መቻሉ ብቻ ነው። አሁን ለረጅም ጊዜ ችላ ከመባሉ ብዛት ችግሩ ነቀርሳ ሆኗል። ለገዥዎቻችን መፍትሄውም ከጃቸው ወጥቷል። ህዝብ ብሄራዊ ውርደትና በያንዳንዱ ዜጋ ላይ የተሰነዘረ ጥቃት አድርጎ ወስዶታል። ለወያኔዎችና ደጋፊዎቻቸው የቀራቸውና ማምለጫው መንገድ በጊዜ ማቄን ጨርቄን ሳይሉ መሸሽ ብቻ ነው እላለው።

ይህ ፅሁፍ ለፕሮፌሰር ተኮላ ሀጎስ  ባደባባይ የተሰጠ መልስም  ተደርጎ ይወሰደልኝ። ጊዜው አንዳንድ መያዝን ይሻል።  የሚቀናቀን ካልመጠ ተመችተውኝ ቀድሜ ይዣቸዋለው።   ወደፊትም በፃፉ ቁጥር መልስ እሰጣለው። የበዛው አንባቢ ዘረኝነት ፃያፍ የሰውን ልጅ ፍረድና አመለካከት ምን ያህል እንደሚያዛባ ያውቃል። ዘረኝነትን ግን እስከ ቦርቃቃ አፉ፤ አስከ ስድስት እግሩ፤ አስከ ጥፍራም እጆቹና እስከ ተንጨባረረ ፀጉሩ አውሬውን ማየት ከፈለጋችሁ የኚህን እውቅ ፕሮፌሰር ፅሁፎች አንብቡ። በቅርቡ አቦጊዳ ላይ የወጣላቸው ፅሁፋቸው አውሬውን በደንብ ልታዩበት የምትችሉበት ነው።

 

Pen

 


ለባለስልጣናት እንጸልያለን፤ ግፍን ግን አንታገስም ! ግርማ ካሳ

$
0
0

Muziky68@yahoo.com

triad candles croppedበቅርቡ በአቶ አቶ ኃይለማሪያም ደሳለኝ ላይ ጠንካራ ትችት ያዘለ ጽሁፍ ለአንባቢያን አቅርቤ ነበር። አዉራምባ ታይምስ ጽሁፌን «What’s the hell is wrong with Haile Mariam Desalegn”  በሚል ርዕስ  ነበር ለአንባቢያኑ ያቀረበዉ። ይህ  ርዕስ ፣  የአዉራምባ ታይምስ ኤዲተር ምርጫ እንጂ የኔ እንዳልሆነ በቅድሚያ እንዲታወቅልኝ እፈልጋለሁ።

አቶ ኃይለማሪያም ደሳለኝ ብዙዎች እንደ «እግዚአብሄር ሰው» ይቆጥሯቸዋል። በየቀኑ ጸሎት እንደሚያደርጉ፣ መጽሃፍ ቅዱስን እንደሚያነቡም ይናገራሉ። እርግጥ ነዉ፣ ሰዎች ጸሎት ሲያደርጉና መጽሃፍ ቅዱስ ሲያነቡ፣  መልካም ነዉ። ነገር ግን ጸሎት ማድረግና መጽሃፍ ቅዱስ ማንበብ፣ በራሱ የእግዚአብሄር ሰው ያሰኛል ብዬ አላስብም። ቄስ፣ ወንጌላዊ፣ ፓስታር፣ ጳጳስ ..መሆን የእግዚአብሄር ሰው አያሰኝም። መስቀል ይዞ መዞር፣ በያሬዳዊ ዜማ ቅኔ መዝረፍ፣ በልሳን መጸለይ ….የእግዚአብሄር ሰዉነት መመዘኛ አይደለም።

አቶ ኃይለማሪያም ደሳለኝ፣ የተባረኩ ሴት ልጆች አሏቸው። ልጆቻቸው፣ የሚኒስቴር ልጆች ሆነዉ እያሉ፣ ሳይኮሩ፣ ከሌሎች በላይ ለመሆን ሳይሞክሩ፣  በሚሄዱበት ቤተ ክርስቲያን፣ እሁድ ከአምልኮ/ቅዳሴ  በኋላ፣  ሻሂ እያፈሉ ምእመናንን እንደሚያስተናግዱ አንብቢያለሁ። በአባታቸው ስልጣን፣ በሶሻል ስታተሳቸው ሳይመኩ፣ እራሳቸዉን አዋርደዉ፣  ሌላዉን ማገለገል መቻላቸዉ፣ በርግጥ የልጅ ትልቅ መሆናቸውን ያሳያል። የእግዚአብሄር ሰዉነት መመዘኛ እንግህ ይሄ አይነቱ ትህትና የተሞላበት ተግባር ነዉ። (የአቶ ኃይለማሪያም ባለቤት ወ/ሮ ሮማንም፣ ከአንድ አመት በፊት ቀዳማዊ እመቤት ከነበሩት የሰማይና ምድር ያህል የሚራራቁ፣   እንደ ቀድሞ ቀዳማዊት እመቤት ዉብአንቺ ቢሻዉ፣ ትሁትና ሰው አክባሪ እንደሆኑ ይነግራል )

አንድ ጊዜ እንዲህ ሆነ። አንድ ሰው ከኢያሪኮ ወደ ኢየሩሳሌም ሲጓዝ ወንበዴዎች አገኙትና በሕይወትና  በሞት መሃከል እስኪሆን ድረስ ደብድበዉት ሄዱ። ሃዘኔታና ርህራሄ የሌላቸው፣ ሌሎች ሲሰቃዩና ሲጎዱ ምንም የማይመስላቸው፣ የሰው ልጅ ስብእናና ክብር እንደ መጫወጫ ካርታ የሆነባቸው፣ ሰዉን በዉሸት ክስ የሚያስሩ፣ እየተኮሱ የሚገድሉና የሚደበድቡ፣ በሰላማዉያን ላይ ሽብር በመንዛት፣ ሰዎች  በሰላም ወጥተዉ በሰላም እንዳይገቡ፣ የፈለጉትን እንዳይጽፉና እንዳይናገሩ፣ በአገራቸው እንደ ስደተኖች እንዲሆኑ የሚያደርጉ፣ እያስፈራሩ ሌላዉን የሚያሸማቅቁ፣ የዘመናችን «ወንበዴዎች» በአገራችን ኢትዮጵያ ብዙ አሉ። እንደዉም በስፋት በየሬዲዮና ቴሌቭዥኑ የምንሰማዉ እነርሱን ነዉ።

በመንገድ ዳር የወደቀውና የተደበደበው፣ የሚረዳው ፈልጎ እያቃሰተ ሳለ፣  ድንገት አንድ ቄስ/ፓስተር በመንገድ ዳር አለፉ። ካባ ለብሰዋል። በታላላቅ መንፈሳዊ ጉባኤዎች የእግዚአብሄርን ቃል የሚያስተምሩ፣ መጽሃፍ ቅዱስ የሚያነቡና ፣ የ«እግዚአብሄር ሰው» የሚባሉ ናቸው።  ነገር ግን የቆሰለዉን ሰው ባዩ ጊዜ እንዳላየ ሆኑ። መንገድ ቀይረው ፣ ለተገፋዉና ለተጎዳው እጃቸውን ሳይዘረጉ ጉዟቸውን ቀጠሉ። ትንሽ ቆይቶም አንድ ሌዋዊ (ዲያቆን)፣ ትንሹ የ«እግዚአብሄር ሰው»  መጣ። እርሱም እንደ ቄሱ እንዳላየ ሆነ አልፎ ሄደ።

ሳምራዊያን የሚባሉ ነበሩ። እግዚአብሄርን እንደማያውቁ ሐጢያተኞችና የረከሱ  ተደርገዉ የሚቆጠሩ።  ታዲያ አንድ ሳምራዊ፣  በወንበዴዎች ተደብድቦ የወደቀዉ ሰው ባለበት መንገድ አለፈ። ቁስለኛዉን ሲያይ ቆመ። ከበቅሎው ወረደ። ተጎነበሰ። ከአንገቱ ሰዉዬን ደግፎ፣ የያዘዉን ወይን ጠጭና ዘይት በሰዉዬዉ ቁስል ላይ አፈሰሰ። ሽሚዙን ቀደደና የሰዉዬዉን ቁስል አሸገ። ሰዉዬን ተሸክሞ በበቅሎው ላይ ጭኖ፣  እርሱ ግን በእግሩ፣  አብረው መንገድ ጀመሩ።  ቁስለኛዉን ወደ አንድ ሆቴል ቤት ገንዘብ ከፍሎ አሳረፈ። አስገራሚ ፍቅር ! አስገራሚ ሰብዓዊነት ! አስገራሚ ርህራሄ ! ይህ ታሪክ፣  ጌታችን መድሃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ፣  የእግዚአብሄር ሰዉ፣  ምን ማለት እንደሆነ ለማስተማር የተናገረው ግሩም ታሪክ ነዉ። ቄሱ፣ ወይንም ዲያቆኑ ሳይሆኑ፣  «የእግዚአብሄር ሰዉ አይደለም» ተብሎ ይቆጠር የነበረው ሳምራዊዉ ነበር፣  በአምላክ ሚዛን የእግዚአብሄር ሰው የተባለው።

በመጽሃፍ ቅዱስ ፣ ኢሳያስ 1፡ 16 እንደተጻፈው፣ እግዚአብሄር ምን ያህል የፍትህ አምላክ እንደሆነ፣ ሲናገር «መባዎቻችሁንና ሰንበታችሁን፣ በጉባኤ መሰብሰባችሁን አልወደዉም። በደልንም የተቀደሰዉንም ጉባኤ አልታገስም። መባዎቻችሁንና በዓላቶቻችሁን ነፍሴ ጠልታለች። ሸክም ሆነዉብኛል። ልታገሳችሁ ደክሜያለሁ።  እጆቻችሁን ወደ እኔ ብትዘረጉ፣ አይኔን ከእናንተ እሰዉራለሁ። ልመናንም ብታበዙ አልሰማችሁም …. ፍርድን ፈልጉ። የተገፋዉን አድኑ። ለድሃ አደጉ ፍረዱለት፤  ስለመበለቲቱም ተሟገቱ። » ነበር ያለው። ከሚደረጉ ዉጫዊና ሃይማኖታዊ ስርአቶች በላይ፣ እግዚአብሄርን የሚያስደስተው፣  የሰዉ ልጆች ደህንነትና ስብእና ነዉ።   አስር ሺህ ቅዳሴዎችና መንፈሳዊ ጉባኤዎች ይልቅ ፣ አንድን ሰው ከወደቀበት ማንሳት፣ አንድን በግፍና በዉሸት የታሰረን ሰው ማስፈታት፣ አንድ የተገፋና የተጮቆነን ሰው ቀንበር መስበር፣ አንድን ሰዉ ማዳን፣  በጌታ ፊት የበለጠ ክብር አለው። የእግዚአብሄር ሰው መሆን ማለት፣  ለፍትህ መቆም ማለት ነዉ። የእግዚአብሄር ሰው መሆን ማለት  ሙግት መፍጠር (መታገል) ማለት ነዉ። ምን አይነት ሙግት ?  የተቀደሰ ፣ ስድብና ጥላቻ የሌለበት፣  ሰላማዊ የሆነ፣  ለፍትህ የሚደረግ ሙግት!

በአገራችን ኢትዮጵያ ያሉ፣ ልንታገልላቸው ወይንም ልንሟገትላቸው የሚገባ  «መበለቶች» ብዙ ናቸው። ገዢዎች ከሚፈልጉት ዉጭ በመናገራቸው፣ እዉነትንና እኩልነትን በመስበካቸው ፣ በዉሸት ክስ፣  «ሽብርተኞች» ተብለው በወህኒ የተወረወሩ፣ ፍርድና ፍትህ የተነፈጉ ሁሉ «መበለቶች» ናቸው።  ሙስሊም ሊሆኑ ይችላሉ፣  ከርስቲያኖች ሊሆኑ ይችላሉ! ኦሮሞ፣ ትግሬ፣ ወላይታ ሊሆኑ ይችላሉ! ጉዳዩ የሰብአዊነት እንጂ የሃይማኖት ወይንም የዘር አይደለም።

ለምሳሌ እነ እስክንደርን እንዉሰድ። በግለሰብ ደረጃ እስክንድር ነጋን እና አንዱዋለም አራጌን አውቃቸዋለሁ። ብዙ ጊዜ በአገራችን ዙሪያ የተለያዩ ሃሳቦችን በግል ተለዋውጠናል። ስለ ትጥቅ ትግል፣ ስለ ግንቦት ሰባት ወዘተረፈ ያላቸውን አመለካከት በሚገባ አውቃለሁ። የጻፉትን እና በአደባባይ የተናገሩትን ተከታትያለሁ። የነርሱን አገር ወዳድነትና ሰላማዊነት፣ በየትኛዉም ፍርድ ቤት ሆነ አደባባይ፣  እጆቼን መጽህፍ ቅዱስ ላይ ጭኔ የምመሰክረው ነዉ።  እግዚአብሄርን  የሚወዱ፣ ቤተሰባቸዉን የሚወዱ፣ በአገራችን እርቅና ሰላም እንዲመጣ የሚናፍቁ፣ ማንም የማያነቃንቃቸው የሰላም አርበኞች ናቸው።  እስክንድርና አንድዋለም እንዲሁም ሌሎች የሕሊና እሥረኞች የአገራችን «መበለቶች» ናቸው። እስክንደርና አንዱዋለም እንዲሁም ሌሎች፣ በመንገድ ዳር ወንበዴዎች እንደደበደቡት ሰዉዬ ናቸው።

እንግዲህ «መጽሃፍ ቅዱስን እናነባለን፤ እግዚአብሄርን እናምናለን. ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስን እንከተላለን» ካልን፣   እየመረጥን አይደለም እግዚአብሄርን የምንታዘዘው። ለተገፉ፣ ለወደቁ፣ በዉሸት ለታሰሩ፣ ፍትህ ለተነፈጉ፣  ወገኖቻችን መቆም መጀመር አለብን።  በጣም አሰምርበታለሁ። ለታሰሩ እስረኞች መቆም ክርስትና ነዉ !  ለፍትህ ለዜጎችን ነጻነት መቆም፣  መጽሃፍ ቅዱሳዊ ነዉ። የእግዚአብሄርን ቃል መታዘዝ ነዉ።

በአንጻሩ፣ ግፍ፣ ቀንበር፣ ጭቆና እያየን፣  ዝምታን ከመረጥን፣ የእግዚአብሄር ቃል እንደሚለዉ  መባዎቻችንና ሰንበታችሁን በጉባኤ መሰብሰባችንን እግዚአብሄር አይወደዉም። እጆቻችንን ወደ እርሱ ብንዘረጋ፣ አይኖቹን  ከእኛ ይሰዉራል።  ልመናንም ብናበዛ አይሰማንም።  ሌላዉ በግፍ ሲታሰር ዝም ማለት፣ ከራሳችን ጥቅምና ምቾት አልፈን አለመሄድ፣ የዘመኑ ጡንቸኞችን ቢያስደስትም፣ ጥቂት ፍርፋሬዎች ቢወረወርልንም፣  የዘላለም አምላክ እግዚአብሄርን  የማያስደስት  እርግማን ነዉ። ነዉር ነው።

አንዳንዶች የመንግስት ባለስልጣናት ላይ ተቃዉሞ ማንሳታችንን ተገቢ እንዳልሆነ ለማሳየት፣ ከመጽሃፍ ቅዱስ አንድ ጥቅስ ነጥለው በማውጣት ለማስተማር የሚሞክሩ፣ ቄስ/ፓስተር ተብዬ የአገዛዙ ካድሬዎች አሉ።  «ለባለስልጣን ጸልዩ፣ ታዘዙ» ተብሎ ስለተጻፈ «ፖለቲካ ዉስጥ ሳንገባ ፣ ታዘን መኖር ነው ያለብን» ይሉናል። አዎ ፣ በዚህ ምክንያት የአገሪቷን ሕግ እናከብራለን። ግብር በጊዜው እንከፍላለን። በትክክል የአገሪቷን ሕግ ከጣስን መቀጣታችን ተገቢ ነዉ እንላለን። ለአቶ ኃይለማሪያም ፣ ልቦና እንዲሰጣቸው፣ በልጆቻቸው ያለው የርህራሄና የፍቅር መንፈስ በርሳቸውም እንዲሰርጽ ፣ አብረዋቸው ያሉ የሰይጣን መልእክተኖችን ሳይሆን የእግዚአብሄርን መንፈስ ማዳመጥ እንዲጀምሩ፣ ሕዝብን ማስተዳደር የሚችሉበት ጥበብ  ጌታ እንዲሰጣቸው ሊጸለይላቸው ይገባል። እኛም እንጸልያለን።

ነገር ግን ባለስልጣናት ግፍ ሲፈጽሙ፣ ለነርሱ እንደምንጸልየዉ ሁሉ ፣ እነርሱን መሟገትንና መታገል  የግድ ነዉ። ነብዬ ናታን ንጉስ ዳዊት ስልጣኑን ተጠቅሞ የሰው ሚስት ደፍሮ፣ የደፈራትም ሴት ነፍሰ ጡር ስትሆን፣  ሐጢያቱን ለመደበቅ ባሏን ባስገደለ ጊዜ፣  ንጉሱን  ፊት ለፊት አወገዘ፣ ተቃወመ። «ለባለስልጣን ታዘዝ» ተብያለሁ ብሎ ዝም አላለም። ንጉስ ሄሮድስ አንቲጳስ፣ የወንድሙን ፊሊጵስ ሚስት ሄሮድያዳን ነጥቆ የራሱ በማድረግ ጸያፍ ተግባር በፈጸመ ጊዜ፣ መጥምቁ ዮሐንስ፣ በአደባባይ ነዉ «ንስሐ ግባ»  ብሎ ያወገዘዉ።  በዚህም ምክንያት ሄሮድስ የመጥምቁን አንገት ሁሉ አስቆርጧል።

የእምነት ሰው መሆን ማለት፣  ባርነትን መቀበል ማለት አይደለም። የእምነት ሰው መሆን ማለት አደርባይ መሆን አይደለም። የእምነት ሰው መሆን ማለት የፍትህ፣ የሰላምና  የነጻነት አርበኛ መሆን ማለት ነዉ። የእምነት ሰው መሆን ማለት እንደነ ነብዩ ናታን፣  ባለስልጣናት ስልጣናቸውን ተጠቅመዉ የሚፈጽሙትን ግፍ ማውገዝና መቃወም ማለት ነዉ። እነ ነብዩ ናታን እንዳደረጉት እኛም፣ ግፍን በምናወግዝበት ጊዜ፣ «እግዚአብሄርን እናምናለን»  የሚሉ ሊቀላቀሉን ይገባል እንጂ ዝም እንድንል ሊነግሩን አይገባም።

አቶ ኃይለማሪያምን  እንወዳቸዋለን፤ መልካም ሲሰሩ ፣ ደግፈናቸዋል፤ ወደፊትም እንደግፋቸዋለን። ነገር ግን ክፋታቸውን፣   አይተን ዝም አንልም። በሽብርተኝነት ስም ፍርድ ሲያዛቡ፣  በዜጎች ላይ ሲዝትኑ ዜጎችን ሲያስፈራሩ ዝም አንላቸዉም። «ባርነት ፣ ጭቆና፣ ግፍ፣ ዘረኝነት፣ የሰብአዊ መብት ረገጣ .. በቃ ! »  ብለናል።  ግፍን አንታገስም። ጥቂቶች የሕዝቡን መብት ረግጠው እንዲቀጥሉ አንፈቅድላቸዉም። ይሄን እንሟገታለን፤ ይሄን እንታገላለን። ጆሮ ያለው ይስማ። ልብ ያለው ያስተውል። እግዚአብሄር ልቦናችንን በፍቅሩ፣ አይምሯችንን በጥበቡ ይሙላልን ! አገራችን ኢትዮጵያ እንዲሁም ኤርትራን ይባርከልን !

በሰላማዊ ትግልና ባህሪያቱ -ክፍል አራት (በአቶ ግርማ ሞገስ)

$
0
0

 

Girma Moges

አቶ ግርማ ሞገስ

በአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርት (አንድነት) በሰላማዊ ትግልና ባህሪያቱ ክፍል አራት በአቶ ግርማ ሞገስ በስካይፕ የሚሰጠው ስልጠና ተጠናቋል። ዝርዝሩ ዝቅ ብሎ ቀርቧል።]

አምባገነኖች ስልጣን ላይ ለመቆየት ህጋዊነት፣ የህዝብ ድጋፍ እና ትብብር፣ የአገር ተፈጥሮ እና የኢኮኖሚ ሃብት ባለቤትነት የተባሉትን የፖለቲካ ኃይል ምንጮች መቆጣጠር አለባቸው። የፖለቲካ ኃይል ምንጮች የሚኖሩት ሰማይ ውስጥ ወይንም አምባገነኖች ደም ውስጥ ሳይሆን ባለቤታቸው ከሆነው ህዝብ ጋር እንደሆነ በስልጣና ክፍል ሶስት አጥንተናል። እርግጥ አምባገነኖች በእነዚህ የፖለቲካ ኃይል ምንጮች ላይ ያላቸውን ቁጥጥር የሚያገኙት ህዝብ ፈቅዶላቸው ወይንም ፈርቶዋቸው ወይንም የተወሰነው ህዝብ ፈቅዶላቸው የቀረው ህዝብ ደግሞ ፈርቷቸው ሊሆን ይችላል። ያም ሆነ ይኽ የእነዚህ የፖለቲካ ኃይል ምንጮች ባለቤት እራሱ ህዝብ እንደሆነ ግልጽ ነው። ለዚህም ነው የፖለቲካ ኃይል ምንጭ ማለትም የመንግስት ስልጣን ምንጭ ወይንም ባለቤት ህዝብ ነው የሚባለው። ህዝብ የፖለቲካ ነፃነቱን የሚነጠቀውም ይኽን የፖለቲካ (የመንግስት) ስልጣን ባለቤትነቱን በኃይል በአምባገነኖች ሲነጠቅ ነው። ነፃ ሆኖ የተወለደ የሰው ዘር ለምን ነፃነቱን ለጥቂት አምባገነን ገዢዎች አስረክቦ ካለነፃነት መገዛትን ይቀበላል? የሚለውን ጥንታዊ የፖለቲካ ፈላስፎች እና ተመራማሪዎች ጥያቄ አንስተን በክፍል ሶስት ማጥናታችን ይታወሳል።

 ቀጣዩን ለማንበብ እዚህ ይጫኑ

Download (PDF, 213KB)

 

Sport: ክርስቲያኖ ሮናልዶ ለባለን ደ ኦር አሸናፊነት የበለጠ ዕድል እንዳለው ተገመተ

$
0
0

ከይርጋ አበበ

ክርስቲያኖ ሮናልዶ ከሦስት ዓመት በፊት የዓለምን ስፖርት አፍቃሪዎች ያነጋገረ የዝውውር ገንዘብ ተመድቦለት ወደ ሪያል ማድሪድ ከተዘዋወረ አንስቶ ስሙ እየገነነ መጥቷል። ክለቡ ማድሪድም ተጫዋቹን የገዛው የልጁን መልከ ቀናነት ተጠቅሞ የማሊያና የምስል ሽያጭ ለመጠቀም አስቦ ነው እስከመባል ደርሶ ነበር። በተጨማሪም ራሱ ሮናልዶ በማንቸስተር ዩናይትድ እንደነበረ ቆይታው ስኬታማ ሊሆን አይችልም የሚል አስተያየትም ተሰንዝሮበት ነበር።

ነገር ግን የ28ዓመቱ ፖርቹጋላዊ ሮናልዶ በስፔኑ ግዙፍ ክለብ ታሪክ መሥራቱን ተያይዞታል። በሪያል ማድሪድ ቆይታው 28ጊዜ ሦስታ (ሃትሪክ) ሲሰራ፣ በድምሩ 218 ጨዋታዎችን ተጫውቶ 227 ኳሶችን ደግሞ ከግብ ማሳረፍ የቻለ ምርጥ ተጫዋችነቱን አስመስከሯል።
የዓለምአቀፉ እግር ኳስ ማህበር ከፈረንሳዩ ፍራንስ ፉትቦል መጽሔት ጋር በመተባበር በየዓመቱ በሚያዘጋጀው የዓለም ኮከብ ተጫዋቾች ክብር ባለን ደ ኦር ሽልማት ሮናልዶ ለዘንድሮው ሽልማት ከታጩት የመጨረሻዎቹ ሦስት እጩዎች መካከል አንዱ ሆኗል። የፖርቹጋል ብሔራዊ ቡድን ፊታውራሪ የሆነው ሮናልዶ በብዙ የስፖርት ቤተሰቦች ዘንድ የኮከብነት ክብሩ ይገባዋል እየተባለ ይገኛል። ለእዚህ ንግግራቸው ማጠናከሪያ አድርገው ያቀረቡት ደግሞ ተጫዋቹ ከ2013 መባቻ ጀምሮ ባለፉት 11 ወራት ተጫውቶ ያገኛቸውን ድሎች ነው።
የአውሮፓውያን አዲሱ ዓመት ከ20ቀናት በኋላ የሚጀምር ሲሆን አዲሱ ዓመት ከመግባቱ በፊት የክርስቲያኖ ዶ ሳንቶስ አቬሮ ሮናልዶ ገድል ሊጠቀስ ይገባዋል ብለው የሚከራከሩ የልጁ አድናቂዎች እየተናገሩ ናቸው። «ተጫዋቹ በአንድ የውድድር ዓመት በአምስት የአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ ጨዋታዎች ዘጠኝ ግቦችን መረብ ላይ ማሳረፍ የቻለ ተጫዋች ነው። በአንድ የጨዋታ ዘመን (2013ሙሉ ዓመቱን ለማለት ነው) ከሃምሳ በላይ ግቦችን በማስቆጠር ብቸኛው ተጫዋች ነው። በስፔን ላሊጋ ከምንጊዜም ሦስታ (ሃትሪክ) አስቆጣሪዎች መስመር ሁለተኛው ተጫዋች ነው» የሚሉትን ነጥቦች አንስተው ይከራከራሉ።
Ronaldo Christiano
በሪያል ማድሪድ እግር ኳስ ክለብ ታሪክ ከምንጊዜም ከፍተኛ ግብ አስቆጣሪ የክለቡ ባለውለታዎች ጎራ የተቀላቀለው ክርስቲያኖ ሮናልዶ ባለፈው ማክሰኞ ምሽት ክለቡ ሪያል ማድሪድ በአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ የመጨረሻ የምድብ ጨዋታ ወደ ቤልጄም ተጉዞ የቤልጀሙን ኮፐን ሀገንን ሁለት ለባዶ ሲረታ ያስቆጠራት ግብ ሌላ ታሪክ እንዲሠራ ምክንያት ሆናለታለች። ይህች ግብ ተጫዋቹን በአውሮፓ ሻምፒዮንስ ሊግ የምድብ ጨዋታዎች ዘጠኝ ግቦችን በማስቆጠር ብቸኛው ተጫዋች እንዲሆን አስችላዋለች።
ከዚህ ቀደም ከሮናልዶ ጋር ተስተካካይ ክብረወሰን የነበራቸው ዝላታን ኢብራሞቪች፣ ፍሊፖ ኢንዛጊ፣ ሩድ ቫን ኒስትሮይ እና ሄርናን ክሪስፖ ሲሆኑ፣ ሮናልዶ ከእነዚህ ተጫዋቾች በአንድ ግብ በመላቅ ብቸኛው ተጫዋች ሊሆን ችሏል።
ክርስቲያኖ ሮናልዶ በ13 የስፔን ፕሪሜራ ሊጋ ጨዋታዎች 17 ግቦችን በማስቆጠር የፒቺቺውን ውድድር እየመራ ይገኛል።

A full list of the Ballon d’Or winners and runners-up since 1956.

1956

1st Stanley Matthews (English, Blackpool)
2nd Alfredo Di Stefano (Argentinean, Real Madrid)
3rd Raymond Kopa (French, Real Madrid)

1957
1st Alfredo Di Stefano (Argentinean, Real Madrid)
2nd Billy Wright (English, Wolverhampton Wanderers)
3rd= Duncan Edwards (English, Manchester United)
3rd= Raymond Kopa (French, Real Madrid)

1958
1st Raymond Kopa (French, Real Madrid)
2nd Helmut Rahn (West German, Rot-Weiss Essen)
3rd Just Fontaine (French, Stade Reims)

1959
1st Alfredo Di Stefano (Argentinean, Real Madrid)
2nd Raymond Kopa (French, Real Madrid)
3rd John Charles (Welsh, Juventus)

1960
1st Luis Suarez (Spanish, Barcelona)
2nd Ferenc Puskas (Hungarian, Real Madrid)
3rd Uwe Seeler (West German, Hamburg)

1961
1st Omar Sivori (Argentinean, Juventus)
2nd Luis Suarez (Spanish, Inter Milan)
3rd Johnny Haynes (English, Fulham)

1962
1st Josef Masopust (Czechoslovakian, Dukla Prague)
2nd Eusebio (Portuguese, Benfica)
3rd Karl-Heinz Schnellinger (West German, Koln)

1963
1st Lev Yashin (Soviet Union, Dynamo Moscow)
2nd Gianni Rivera (Italian, AC Milan)
3rd Jimmy Greaves (English, Tottenham Hotspur)

1964
1st Denis Law (Scottish, Manchester United)
2nd Luis Suarez (Spanish, Inter Milan)
3rd Amancio (Spanish, Real Madrid)

1965
1st Eusebio (Portuguese, Benfica)
2nd Giacinto Facchetti (Italian, Inter Milan)
3rd Luis Suarez (Spanish, Real Madrid)

1966
1st Bobby Charlton (English, Manchester United)
2nd Eusebio (Portuguese, Benfica)
3rd Franz Beckenbauer (West German, Bayern Munich)

1967
1st Florian Albert (Hungarian, Ferencváros)
2nd Bobby Charlton (English, Manchester United)
3rd Jimmy Johnstone (Scottish, Celtic)

1968
1st George Best (Irish, Manchester United)
2nd Bobby Charlton (English, Manchester United)
3rd Dragan Džajić (Yugoslavian, Red Star Belgrade)

1969
1st Gianni Rivera (Italian, AC Milan)
2nd Luigi Riva (Italian, Cagliari)
3rd Gerd Muller (West German, Bayern Munich)

1970
1st Gerd Muller (West German, Bayern Munich)
2nd Bobby Moore (English, West Ham United)
3rd Luigi Riva (Italian, Cagliari)

1971
1st Johan Cruyff (Dutch, Ajax)
2nd Sandro Mazzola (Italian, Inter Milan)
3rd George Best (Irish, Manchester United)

1972
1st Franz Beckenbauer (West German, Bayern Munich)
2nd Gerd Muller (West German, Bayern Munich)
3rd Gunter Netzer (West German, Borussia Monchengladbach)

1973
1st Johan Cruyff (Dutch, Barcelona)
2nd Dino Zoff (Italian, Juventus)
3rd Gerd Muller (West German, Bayern Munic)

1974
1st Johan Cruyff (Dutch, Barcelona)
2nd Franz Beckenbauer (West German, Bayern Munich)
3rd Kazimierz Deyna (Polish, Legia Warsaw)

1975
1st Oleg Blokhin (Soviet Union, Dynamo Kiev)
2nd Franz Beckenbauer (West German, Bayern Munich)
3rd Johan Cruyff (Dutch, Barcelona)

1976
1st Franz Beckenbauer (West German, Bayern Munich)
2nd Rob Rensenbrink (Dutch, Anderlecht)
3rd Ivo Viktor (Czechoslovakian, Dukla Prague)

1977
1st Allan Simonsen (Danish, Borussia Monchengladbach)
2nd Kevin Keegan (English, Hamburg)
3rd Michel Platini (French, Nancy)

1978
1st Kevin Keegan (English, Hamburg)
2nd Hans Krankl (Austrian, Barcelona)
3rd Rob Rensenbrink (Dutch, Anderlecht)

1979
1st Kevin Keegan (English, Hamburg)
2nd Karl-Heinz Rummenigge (West German, Bayern Munich)
3rd Ruud Krol (Dutch, Ajax)

1980
1st Karl-Heinz Rummenigge (West German, Bayern Munich)
2nd Bernd Schuster (West German, Real Madrid)
3rd Michel Platini (French, Saint-Etienne)

1981
1st Karl-Heinz Rummenigge (West German, Bayern Munich)
2nd Paul Breitner (West German, Bayern Munich)
3rd Bernd Schuster (West German, Barcelona)

1982
1st Paolo Rossi (Italian, Juventus)
2nd Alain Giresse (French, Bordeaux)
3rd Zbigniew Boniek (Polish, Juventus)

1983
1st Michel Platini (French, Juventus)
2nd Kenny Dalglish (Scottish, Liverpool)
3rd Allan Simonsen (Danish, Vejle)

1984
1st Michel Platini (French, Juventus)
2nd Jean Tigana (French, Bordeaux)
3rd Preben Elkjær (Danish, Verona)

1985
1st Michel Platini (French, Juventus)
2nd Preben Elkjær (Danish, Verona)
3rd Bernd Schuster (West German, Barcelona)

1986
1st Igor Belanov (Soviet Union, Dynamo Kyiv)
2nd Gary Lineker (English, Barcelona)
3rd Emilio Butragueño (Spanish, Real Madrid)

1987
1st Ruud Gullit (Dutch, AC Milan)
2nd Paulo Futre (Portuguese, Atletico Madrid)
3rd Emilio Butragueño (Spanish, Real Madrid)

1988
1st Marco van Basten (Dutch, AC Milan)
2nd Ruud Gullit (Dutch, AC Milan)
3rd Frank Rijkaard (Dutch, AC Milan)

1989
1st Marco van Basten (Dutch, AC Milan)
2nd Franco Baresi (Italian, Milan)
3rd Frank Rijkaard (Dutch, Milan)

1990
1st Lothar Matthaus (German, Inter Milan)
2nd Salvatore Schillaci (Italian, Juventus)
3rd Andreas Brehme (German, Inter Milan)

1991
1st Jean-Pierre Papin (French, Marseille)
2nd= Dejan Savicevic (Yugoslavian, Red Star Belgrade)
2nd= Darko Pancev (Yugoslavian, Red Star Belgrade)
2nd= Lothar Matthaus (German, Bayern Munich)

1992
1st Marco van Basten (Dutch, AC Milan)
2nd Hristo Stoichkov (Bulgarian, Barcelona)
3rd Dennis Bergkamp (Dutch, Ajax)

1993
1st Roberto Baggio (Italian, Juventus)
2nd Dennis Bergkamp (Dutch, Inter Milan)
3rd Eric Cantona (French, Manchester United)

1994
1st Hristo Stoichkov (Bulgarian, Barcelona)
2nd Roberto Baggio (Italian, Juventus)
3rd Paolo Maldini (Italian, AC Milan)

1995
1st George Weah (Liberian, AC Milan)
2nd Jurgen Klinsmann (German, Bayern Munich)
3rd Jari Litmanen (Finnish, Ajax)

1996
1st Matthias Sammer (German, Borussia Dortmund)
2nd Ronaldo (Brazilian, Barcelona)
3rd Alan Shearer (English, Newcastle United)

1997
1st Ronaldo (Brazilian, Inter Milan)
2nd Predrag Mijatović (Yugoslavian, Real Madrid)
3rd Zinedine Zidane (French, Juventus)

1998
1st Zinedine Zidane (French, Juventus)
2nd Davor Suker (Croatian, Real Madrid)
3rd Ronaldo (Brazilian, Inter Milan)

1999
1st Rivaldo (Brazilian, Barcelona)
2nd David Beckham (English, Manchester United)
3rd Andriy Shevchenko (Ukrainian, AC Milan)

2000
1st Luis Figo (Portuguese, Real Madrid)
2nd Zinedine Zidane (French, Real Madrid)
3rd Andriy Shevchenko (Ukrainian, AC Milan)

2001
1st Michael Owen (English, Liverpool)
2nd Raul (Spanish, Real Madrid)
3rd Oliver Kahn (German, Bayern Munich)

2002
1st Ronaldo (Brazilian, Real Madrid)
2nd Roberto Carlos (Brazilian, Real Madrid)
3rd Oliver Kahn (German, Bayern Munich)

2003
1st Pavel Nedved (Czech, Juventus)
2nd Thierry Henry (French, Arsenal)
3rd Paolo Maldini (Italian, AC Milan)

2004
1st Andriy Shevchenko (Ukrainian, AC Milan)
2nd Deco (Portuguese, Barcelona)
3rd Ronaldinho (Brazilian, Barcelona)

2005
1st Ronaldinho (Brazilian, Barcelona)
2nd Frank Lampard (English, Chelsea)
3rd Steven Gerrard (English, Liverpool)

2006
1st Fabio Cannavaro (Italian, Real Madrid)
2nd Gianluigi Buffon (Italian, Juventus)
3rd Thierry Henry (French, Arsenal)

2007
1st Kaka (Brazilian, AC Milan)
2nd Cristiano Ronaldo (Portuguese, Manchester United)
3rd Lionel Messi (Argentinean, Barcelona)

2008
1st Cristiano Ronaldo (Portuguese, Manchester United)
2nd Lionel Messi (Argentinean, Barcelona)
3rd Fernando Torres (Spanish, Liverpool)

2009
1st Lionel Messi (Argentinean, Barcelona)
2nd Cristiano Ronaldo (Portuguese, Real Madrid)
3rd Xavi Hernandez (Spanish, Barcelona)

FIFA Ballon d’Or

2010
1st Lionel Messi (Argentinean, Barcelona)
2nd Andres Iniesta (Spanish, Barcelona)
3rd Xavi Hernandez (Spanish, Barcelona)

2011
1st Lionel Messi (Argentinean, Barcelona)
2nd Cristiano Ronaldo (Portuguese, Real Madrid)
3rd Xavi Hernandez (Spanish, Barcelona)

2012
1st Lionel Messi (Argentinean, Barcelona)
2nd Cristiano Ronaldo (Portuguese, Real Madrid)
3rd Andres Iniesta (Spanish, Barcelona)

አርሰናል በማን. ሲቲ ግማሽ ደርዘን ጎል ገባበት (All Goals & Highlights)

$
0
0

የአርሰናል እና የማን.ሲቲ ጨዋታ ጎሎች እና የጨዋታውን ሃይላይት እነሆ፦

Manchester City vs Arsenal (6-3) All Goals & Highlights 914.12.2013] by Mojogoals
99cab68bfe5d90795d3b37d36741c4d8_M
በ16ኛው ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሜርሊግ የሊጉ መሪ አርሰናል ወደ ኢትሃድ አቅንቶ ማንቸስተር ሲቲን ቢያስተናግድም የ6ለ3 ሽንፈት ገጥሞታል፡፡ ሲቲ የሊጉን መሪ አርሰናልን ማሸነፍ በመቻሉ በሊጉ በ3 ነጥብ ልዩነት በ3ኛ ደረጃ መቀመጥ ችሏል፡፡
የአርሰናል አስደናቂ አጀማምር በተከታታይ ባደረጋቸው ሶስት ጨዋታዎች ደብዝዞ ታይቷል፡፡ ፈርናንዲኒሆ ሁለት፣ አጉየሮ፣ ኔግሬዶ፣ ሲልቫና ያያ ቱሬ አንዳንድ ጎሎችን በስማቸው ከመረብ አገናኝተዋል፡፡

አርሰናል ኳስን ይዞ በመጫወት በኩል ብላጫ ስለተወሰደበት ለሲቲ አጥቂዎች ምቹ ሆኖ አምሽቷል፡፡ ዋልኮት ሁለት ጎሎችን ከመረብ በማገናኘት ሁለት ጊዜ አርሰናልን አቻ ቢያደርግም ሲቲ በመልሶ ማጥቃት የአርሰናልን መረብ በተደጋጋሚ መፈተሽ ችሏል፡፡መርቲ ሳከር ለአርሰናል ቀሪዋን ጎል ከመረብ አሳርፏል፡፡ አርሰናል በሳምንቱ በሻምፒዮንስ ሊግ በጣሊያኑ ናፖሊ 2ለ0 ተሸንፎ መመለሱ ይታወሳል፡፡ ማንችስትር ሲቲ በተመሳሳይ ባለፈው ሳምንት በግማሽ ደርዘን ጎል ቶተናምን አሸንፏል፡፡ ቸልሲ ክሪስታል ፓላስን 2ለ1 በማሸነፍ 2ኛ ደረጃ ይዟል፡፡

“ወደ ፖለቲካው ተመልሻለሁ”–አቶ ልደቱ አያሌው

$
0
0

በምርጫ 97 በፊት ኢትዮጵያዊው ማንዴላ ተብለው እንዳልተሞካሹ ሁሉ ከምርጫ 97 በኋላ በኢትዮጵያ ፖለቲካ ውስጥ አይንህ ለአፈር ከተባሉት ፖለቲከኞች መካከል አንዱ እንደሆኑ የሚነገርላቸው የቀድሞው የኢዴፓ ሊቀመንበር አቶ ልደቱ አያሌው ወደ ፖለቲካው መመለሳቸውን አስታወቁ። “ለትምህርት ከ2 ዓመታት በላይ በውጭ ሃገር በመቆየቴ እንዲሁም ከኢዴፓ ሃያ አምስቱ የማዕከላዊ ኮሚቴ አባላት አንዱ ብሆንም፣ በጠቅላላ ጉባኤ ከሊቀመንበርነት ስለወረድኩ የፓርቲው የዕለት ተዕለት እንቅስቃሴ ስለማልመራ” ከሚድያው ጠፍቻለሁ ያሉት አቶ ልደቱ ወደ ፖለቲካው መመለሳቸውን ያስታወቁት በአዲስ አበባ ከሚታተመው አዲስ አድማስ ጋዜጣ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ ነው።
lidetu
“በኢትዮጵያ ውስጥ የኢኮኖሚ እድገቱን መካድ ስህተት ነው፤ እድገቱ ዘላቂነት እንደሌለው አለመገንዘብም ስህተት ነው” የሚሉት አቶ ልደቱ “ሦስተኛ አማራጭ” የተሰኘ የኢዴፓ አቋምን በቃለ ምልላቸው ላይ ገልጸዋል።

በቃለምልልሳቸው ላይ ኢሕአዴግ አመጣሁት ስለሚለው ዕድገት አቶ ልደቱ “”የእድገቱ መጠን መንግስት እንደሚለው ሳይሆን፣ ስምንትና ሰባት ፐርሰንት ይሆኖል ብዬ አምናለሁ፡፡ ይሄም ቢሆን መጥፎ እድገት አይደለም፤ ጥሩ እድገት ነው፡፡ በእርግጥ በኢትዮጵያ ደረጃ ላለ ድሃ አገር ከስድስት ፐርሰንት በታች የወረደ እድገት፤ ኢኮኖሚው እንደተኛ (ሪሴሽን ውስጥ እንደገባ ነው የሚቆጠረው፡፡ በጣም በከፍተኛ ደረጃ ማደግ ነው የሚጠበቅብን፡፡ የሌሎችም አገራትም ታሪክ ያንን ነው የሚያሳየው፡፡ እንደ አሜሪካና እንደ እንግሊዝ አገር አይነት ትልቅ ኢኮኖሚ ውስጥ ሶስትም አራትም ፐርሰንት ማደግ ከባድ ነው፡፡ እንደ ኢትዮጵያ ዓይነት ኢኮኖሚ ተይዞ ግን፤ ደብል ዲጂት ማደግ ይቻላል፡፡ መጣ የሚባለው እድገት በህብረተሰቡ ህይወት ውስጥ መታየት አልነበረበትም ወይ? ሊታይም ላይታይም ይችላል፡፡ አንድ ኢኮኖሚ ማደግ ሲጀምር ሁሉንም ህብረተሰብ ይጠቅማል ማለት አይቻልም፡፡ ይሄ በየትም አገር ሆኖ አያውቅም፡፡ እንኳን ዘጠና ሚሊዬን ህዝብ ያለበት አገር ይቅርና፣ 3ሚሊዮን ህዝብ ባለበት አገርም ኢኮኖሚው ማደግ ሲጀምር ሁሉም ህብረተሰብ ተጠቃሚ ይሆናል ማለት አይደለም፡፡ ቀስ በቀስ ነው ተጠቃሚው እየበረከተና እያደገ የሚመጣው፡፡ ስለዚህ አሁን ኢትዮጵያ ውስጥ ድህነት ይታያል። ድህነት ብቻ አይደለም በርሃብም የሚሰቃዩ ሰዎች ብዙ ናቸው፡፡ እነዚህ ሰዎች መኖራቸው ግን እድገት የለም ወደሚለው ድምዳሜ አይወስደንም፡፡ እድገትም ባለበት አገር ሰው ይራባል፤ ሰው በድህነት ይማቅቃል፡፡ እንኳን በእኛ በጀማሪ አገር ቀርቶ፣ የዳበረ እድገት አላቸው የሚባሉ አገሮችም የሚቸገሩ ሰዎች አሉ፡፡” ብለዋል።

“መንግስት የሚፈጥረው ጫና ለተቃዋሚዎች መዳከም አንድ ምክንያት ነው እንጂ ብቸኛ ምክንያት አይደለም፡፡” ሲሉ በቃለ ምልልሳቸው ላይ የተናገሩት አቶ ልደቱ “አንድ ተቃዋሚ ፓርቲ እኮ ጠንካራ ነው የሚባለው፤ መንግስት የሚያደርግበትን ተጽዕኖ ተቋቁሞ ማሸነፍ ሲችል ነው፡፡ መንግስት ተጽእኖ የማያደርግ ከሆነማ ሁሉን ነገር የተመቻቸ ከሆነማ ትግልም አያስፈልግም። አገራችን እንደ አሜሪካ ሆናለች ማለት ነው። መንግስት ተፅዕኖ የማያደርግ ከሆነ፣ በጣም የምንመኘው ደረጃ ላይ በቀላሉ ደርሰናል ማለት ነው፡፡ ተዝናንተን በምዕራቡ ዓለም እንደምናየው በምርጫ እየተወዳደርን አሸናፊና ተሸናፊ ልንሆን እንችላለን ማለት ነው፡፡ ግን እዚያ ደረጃ ላይ ለመድረስ ቀርቶ ጨርሶ አልተጠጋንም፡፡ በተቃዋሚ ፓርቲዎች ላይ ጫና የሚያደርግ መንግስት ነው ያለን፡፡ ይህን ለመለወጥም ነው የፖለቲካ ትግል እያካሄድን ያለነው፡፡ ህዝቡን አስተባብረንና አታግለን፤ የመንግስት ጫና እንዲቆምና ለውጥ እንዲመጣ ማድረግ እንችላለን፡፡ ይልቅስ ትልቅ እንቅፋት የሆነብን ውስጣዊ ችግር እንዳለብን መገንዘብ አለማቻላችን ነው፡፡ ውስጣዊ ድክመቶችን ለመፈተሸ አለማድረጋችን ነው ካንሠር ሆኖ የሚበላን፡፡ በ1997 ዓ.ም ምርጫ ተቃዋሚዎች ጥምረት እየፈጠሩ የህዝቡን ትኩረት በመሳብ በምርጫ ውጤት አምጥተዋል፡፡ የፓርቲዎችን ብርቱ ፉክክር የሚያካሂዱበት ነፃነት ተፈጥሮ ነበር፡፡ ለ2007 ዓ.ም ምርጫ ግን ጥምረት የመፍጠር ህዝቡን የማንቀሳቀስና ብርቱ ፉክክር የማካሄድ ሁኔታ ጎልቶ አይታይም፡፡” ብለዋል።

በቀጣይ 2007 በሚደረገው የኢትዮጵያ ምርጫ ላይ “መሰረታዊ ለውጥ ይመጣል ብዬ አላስብም፡፡” የሚሉት አቶ ልደቱ ለዚህም ምክንያታቸው “አንደኛ ነገር ገዢው ፓርቲ ከስህተቱ እየተማረ አይደለም፡፡ አሁንም በየቀኑ የሚነግረን፤ ዲሞክራሲ ኢትዮጵያ ውስጥ ዲሞክራሲ ሞልቶ እንደተትረፈረፈና ተቃዋሚ ፓርቲዎች እንቅስቃሴ ለማድረግ ምንም ችግር እንደሌላቸው ነው፡፡ ይህቺ አገር በልማት ብቻ ሳይሆን በዲሞክራሲም እያደረገች እንደሆነ ነው ኢህአዴግ የሚነግረን። ይሄ ቀልድ ነው፡፡ በተጨባጭ ያለው ሁኔታ ኢህአዴግ እንደሚለው አይደለም፡፡ የዲሞክራሲ ስርዓት በአግባቡ በዚች አገር እንዲያብብ እያደረገ አይደለም። ገዢው ፓርቲ ላይ ቁርጠኝነት እየታየ አይደለም፡፡ በተቃዋሚ ፓርቲዎች በኩልም አብዛኛው ውስጣዊ ድክመታቸውን ሳይፈትሹ ነባሩን አስተሳሰብና አቀራረብ እንደያዙ ናቸው፡፡ ስለዚህ በ2007 ዓ.ም ምርጫ፣ መሠረታዊ ለውጥ ያመጣል የሚል እምነት የለኝም፡፡ መሠረታዊ ለውጥ ቢመጣ የሚችለው እነዚህ ሁለት ጐራዎች ከስህተታቸውና ከችግራቸው ተምረው የተግባር ማሻሻያዎችን ሲያደርጉ ነው። ይሄን ሲያደርጉ አይታይም፡፡ አሁን የቀረው አንድ ዓመት ነው፡፡ በዚህ አንድ ዓመት ውስጥ መንገዳቸውን ካላስተካከሉ፣ ምርጫው ከአለፉት ምርጫዎች የተሻለ ይሆናል ብዬ አላምንም፡፡” የሚል ነው።
lidetu-ayalew-and-muse-semu
ዩኒቨርስቲ ኮሌጅ ኦፍ ለንደን ፤ ስኩል ኦፍ ኦሬንታል ኤንድ አፍሪካን ስቴዲስ የሚባል ውስጥ “ዲቨሎፕመንት ስተዲስ አጥንቼ ወደ ሃገሬ ገብቼ መኖር ጀምሬያለሁ ሲሉ ለአዲስ አድማስ ጋዜጣ የተናገሩት አቶ ልደቱ “ከ1997 ዓ.ም. ምርጫ በኋላ ኢዴፓ ‹‹ሶስተኛ አማራጭ›› የሚል ሃሳብ ይዟል፡፡ ይሄ ሃሳባችሁ ከምን አደረሳችሁ?” በሚል ለቀረበላቸው ጥያቄ “ሶስተኛ አማራጭ ሲባል፣ ልዩ የርዕዮተ አለም መስመርን ለመግለጽ ሳይሆን፣ የአቀራረብና የስልት ጉዳይ ነው፡፡ የኢትዮጵያ ፓለቲካ፣ እስከ አሁን ድረስ ሁለት ፅንፍ የያዘ ነው። ሁለትም ነገር መደገፍ ወይም ሁሉንም ነገር መቃወም፡፡ የገዥው ፓርቲ አባል ከተሆነ፤ ተቃዋሚ የሚሰራውን ነገር ሙሉ በሙሉ ማጥላላት፤ የተቃዋሚ አባል ከተሆነ ደግሞ መንግስት የሚሠራውን ነገር ሁሉ መቃወም፡፡ እንዲህ ሁለት ጫፍ የያዘ አሰላለፍ፤ ለአገራችን ፖለቲካ አልጠቀመም፡፡ ከመቻቻል ከመደማመጥ አርቆናል፡፡ ለዚህም ነው፤ ከሁለቱ ጽንፎች የተለየ አማራጭና የተለያየ አቀራረብ ያስፈልጋል የሚል አስተሳሰብ ይዘን የመጣነው፡፡ በመንግስትም ሆነ በተቃዋሚ የተሠራ ነገር ለአገርና ለህዝብ የሚጠቅም ከሆነ ልንደግፈው ይገባል፡፡ የማይጠቅምና የሚጐዳ ከሆነ ደግሞ በተጨባጭ መረጃ መቃወምና እንዲቀየር መታገል ያስፈልጋል፡፡ በስሜታዊ ጽንፍ ሳይሆን በምክንያታዊ አስተሳሰብ ነው ፖለቲካው ሊመራ የሚገባው፡፡ አለበለዚያ፣ የኢትዮጵያ ፖለቲካ ወደ ዲሞክራሲያዊ የመቻቻል ባህል ሊቀየር አይችልም። ሁለት ስሜታዊ ፅንፎችን ይዞ፣ ብሔራዊ መግባባት ለማምጣት በጣም አስቸጋሪ ስለሆነ፣ ምክንያታዊ አስተሳሰብ ነው የሚያዋጣን ብለን ሶስተኛ አማራጭ ይዘናል፡፡ ይሄንን አቀራረብ ይዘን ስንመጣ ፈተናዎች ገጥመውናል፡፡ ሁለቱ ጽንፎች ለረዥም ጊዜ ስር የሰደዱና የከረሩ ስለነበሩ፣ ብዙ ሰዎች የእኛን አስተሳሰብ ለመቀበል በጣም አስቸግራቸዋል፡፡ ደግሞም አያስገርምም፡፡ ሰዎች በቀላሉ ይሄን አስተሳሰብ የሚቀበሉ ከሆነ፤ ከመነሻው የአገራችን ፖለቲካ ከባድ ችግር የለበትም ማለት ነው፡፡ የአገራችን ፖለቲካ ግን ለረዥም ጊዜ የዘለቀ ትልቅ ችግር አለበት፡፡ ስለሆነም፤ ሦስተኛ አማራጭ ብለን ያቀረብነው የምክንያታዊ አስተሳሰብ አቅጣጫችንን ብዙ ሰዎች በቀላሉ ሊቀበሉት አልቻሉም። “ተቃዋሚ ከሆንክ በቃ ማንኛውንም ነገር ትቃወማለህ፡፡ ኢህአዴግም ከሆንክ ማንኛውንም ነገር ትደግፋለህ፤ ሌላ ሦስተኛ አማራጭ የለም” የሚል የተዛባ አመለካከት ይሰነዘርብን ነበር፡፡ “እንዲያውም ሦስተኛው አማራጭ የምትሉት ነገር ወላዋይነት ነው” በማለት ውዥንብር የመፍጠር ነገርም ነበር። በሂደት ግን፣ ብዙ ሰው ጉዳዩን እያብላላው፣ እያጤነውና እየተገነዘበው እንደሆነ አይተናል፡፡ እኛ በምንፈልገው ፍጥነት ህብረተሰቡ ተረድቶታል የሚል እምነት የለንም፡፡ ገና ብዙ ይቀራል፡፡ የኢትዮጵያ ፖለቲካ እስከአሁን በመጣበት የጽንፈኝነት መንገድ የትም ሊያደርሰን እንደማይችል ብዙዎች እየገባቸው ነው፡፡ ሁለቱ ጽንፎች የሚፈጥሩት ቅራኔና ውጥረት፣ ከዴሞክራሲ እያራቀን እንጂ ወደ መቻቻል እያመጣን እንዳልሆነ ሰው እየተገነዘበው ነው፡፡
“ሁለቱ የፅንፍ ሃይሎችና ጐራዎች አይጠቅሙም ትክክል አይደሉም” የሚለው አስተሳሰብ እየጐላ መጥቷል፡፡ “ሁለቱም ፅንፎች አይጠቅሙም፤ ችግር አለባቸው” ከተባለ ክፍተት መኖሩን ነው የሚያሳየው፡፡ ያንን ክፍተት የመሙላት ጉዳይ ነው የሶስተኛው አማራጭ ፋይዳ፡፡ ይሄንን አስተሳሰብ ይዘን እንደነበር በተለይ በፓርላማ በነበረን ተሳትፎ በደንብ ማሳየት ችለን ነበር፡፡ ፓርላማ ውስጥ ሌሎች ተቃዋሚዎች ከሚያራምዱት አስተሳሰብ በተለየ ሁኔታ፣ መንግስት ከሚሠራቸው ነገሮችና ከሚያራምዳቸው አቋሞች ውስጥ ለህዝብና ለሀገር የሚጠቅም ነገር ስናገኛቸው በድፍረት ስንደግፍ ታይቷል፡፡ ሰው ለዛ የሚሠጠው ትርጉም ምንም ይሁን እኛ ለሀገርና ለህዝብ ይጠቅማል ብለን እስካመንበት ድረስ በድፍረት ወጥተን፤ ይሄ አቋም ከገዢው ፓርቲም ይምጣ ከተቃዋሚ ፓርቲም ይምጣ ለአገርና ለህዝብ የሚጠቅም እስከሆነ ድረስ እንደግፋለን ብለን ማሳየት ችለናል፡፡ ገዢው ፓርቲ ጥሩ ያልሆኑ ነገሮችን ሲሰራ ደግሞ ከሌሎች ተቃዋሚዎች በበለጠ በመረጃ በተደገፈ ከመተቸትና በጠነከረ መልኩ በመታገል ምክንያታዊነታችንን ማሳየት ችለናል፡፡ ከተቃዋሚ ፓርቲ ውስጥም ጥፋት ወይም ድክመት ሲኖር፣ ተቃዋሚ ነውና እሱን አንነካውም አንልም፡፡ እንዲስተካከል እንተቻለን፡፡ ለሰላማዊ ትግልና ለአገር የማይበጅ፣ ለመቻቻል ፖለቲካ ማይጠቅም ሆኖ ካገኘነው፣ ተቃዋሚውንም ቢሆን በድፍረት የመተቸት አዲስ ባህል ይዘን መጥተን አሳይተናል፡፡ ያን የማይወዱ ሰዎች ብዙ ነበሩ፡፡
“በሂደት እየተረዱ ሲመጡ፣ ግን እኛ የያዝነው አቋም ትክክል እንደሆነ መገንዘብ የቻሉ ሰዎች ብዙ ናቸው፡፡ ይሄ አቋማችን በአገራችን ያልተለመደ አዲስ አቋምና አካሄድ ስለሆነ፤ አንዳንድ ሰዎች በእኛ ላይ የሚያወሩትን አሉባልታ ማራገብ ተጠቅመውበታል። በእኛ ላይ ከንቱ ጥርጣሬና ጥላቻ እንዲስፋፋ በማድረግ አሉታዊ ተፅዕኖ አሳርፈዋል። በሌላ በኩል ግን ከነባሩ የጽንፈኝነት ፖለቲካ የተለየ ምክንያታዊ ፖለቲካ ማራመድ ለዚህ አገር እንደሚያስፈልግ በደንብ ለማሳየት ችለናል፡፡ ስለዚህ ሦስተኛ አማራጭ ይዘን መምጣታችን፣ ጥቅምም ጉዳትም ነበረው፡፡ ከአጭር ጊዜ አንፃር፣ ሊያስወድድ የሚችል የፖለቲካ አቋም አልነበረም፡፡ ለአሉባልታ አጋልጦናል፡፡ ከረጅም ጊዜ አንፃር ግን ይሄ ምክንያታዊ የፖለቲካ መስመራችን እየሰፋና እያደገ፣ በተለይ በአዲሱ ትውልድ ዘንድ ተቀባይነት እያገኘ የሚመጣ አቋም ነው፡፡ ስለዚህ ጠቀሜታው ከፍተኛ ነው ብዬ ነው የማስበው፡፡ ከጊዜ ወደ ጊዜ የበለጠ እየተጠናከረ ነው፡፡ ግን ሂደቱን እኛ ስለተናገርነውና ስላራመድነው ብቻ ውጤት ያመጣል ማለት አይደል፡፡ ከአጠቃላይ ከአገራቱ ሶሽዬ ኢኮኖሚክ የእድገት ደረጃ ጋር ተያይዞ ነው ተቀባይነት ሊያገኝ የሚችለው፡፡ አንድ የፖለቲካ ፓርቲ ወጥቶ ስለተናገረ ብቻ፣ የበቃ የፖለቲካ አመለካከት ያለው ህብረተሰብ ይፈጠራል ማለት አይደለም፡፡ እንደዛ አይነት ህብረተሰብ የሚመጣው ኢኮኖሚያችን ሲያድግና ሲዳብር፤ ትምህርት ሲስፋፋና ከሌላው አለም ጋር መስተጋብራችን የበለጠ ሲጠናከር ነው፡፡ በአጭር ጊዜ የሚቀየር ነገር አይደለም፡፡ የአስተሳሰብ ለውጥ እውን የሚሆንበት ሂደት በጣም የተራዘመ እንዳይሆንና እንዲፋጠን በማድረግ ረገድ ግን የኢዴፓ ሚና ከፍተኛ ነው፡፡” ሲሉ ሰፋ ያለ ማብራሪያ ሰጥተዋል።

በአቶ ልደቱ ወደ ፖለቲካው መመለስ ዙሪያ የዘ-ሐበሻ ተከታዮች ምን ትላላችሁ?

(ሰበር ዜና) የሚኒሶታው መድሃኔዓለም ቤ/ክ ባለበት በገለልተኛነቱ እንዲቀጥል ተወሰነ

$
0
0

(ዘ-ሐበሻ) በሰሜን አሜሪካ ከሚገኙ ታላላቅ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤ/ክ አንዱ የሆነው የሚኒሶታው ደብረሰላም መድሃኔዓለም ቤ/ክ ለረጅዥም ጊዜ ምዕመናኑን በሁለት ሃሳብ ከፍሎ ሲያወዛግብ የቆየው በሃገር ቤት ያሉት አባቶች እና በውጭ የሚገኙ አባቶች አንድነት እስኪያመጡ ድረስ በገለልተኝነት እንቆይ እና፤ ወደ ሃገር ቤቱ ሲኖዶስ እንጠቃለል የሚለው ሃሳብ ዛሬ ውሳኔ አግኝቷል።
deb
ከግማሽ ቀን በላይ በወሰደው የደብረሰላም መድሃኔዓለም ቤ/ክ አስተዳደር ቦርድ የጠራው ጉባኤ ዛሬ ዲሴምበር 15 ቀን 2013 ዓ.ም የተደረገ ሲሆኑ፤ የቤተክርስቲያኑ አባላት በዚህ ጉዳይ ውሳኔ እንዲሰጡ ተደርጎ በጉባኤው ላይ ከተገኙት ውስጥ በአብዛኛው ድምጽ የሰጡ ምዕመናን በገለልተኛነት እንዲቆይ በመምረጣቸው ቤተክርስቲያኑ እስካሁን እንደነበረው በገለልተኛንቱ እንዲቀጥል ተወስኗል።

በዚህ ጉባኤ ላይ የቤተክርስቲያኒቱ ካህናት ዛሬ ምርጫ እንዳይደረግ ሆኖም ግን የአንድነት ትምህርት እየተሰጠ እንዲቆይ ጥያቄ ማቅረባቸውን ጉባኤው ውስጥ የነበሩ ወገኖች ለዘ-ሐበሻ ገልጸው አብዛኛው ምእመናን ግን የካህናቱን ሃሳብ ውድቅ እንዳደረገው የደረሰን መረጃ ያመለክታል።

በሚኒሶታ የሚገኙ ከ30 ሺህ በላይ ኢትዮጵያውያን ይህን የውሳኔ ቀን በጉጉት ሲጠብቁት የቆየ ሲሆን ውሳኔውን ለማወቅ ዛሬ ሙሉ ቀን የዘ-ሐበሻ ስልክ ሲጨናነቅ ነበር የዋለው።

በዛሬው ጉባኤ ዙሪያ ለዘ-ሐበሻ አንባቢዎች መረጃ እንዲሰጡልን ለቤተክርስቲያኒቱ የሕዝብ ግንኙነት ሃላፊ አቶ መኳንንት ታዬ ከምሽቱ 6:30 ጀምሮ ስልካቸውን ስንደውል የነበረ ሲሆን ስልካቸው ዝግ በመሆኑ ሃሳባቸውን ማካተት አልቻልንም። ሆኖም ግን እንዳገኘናቸው የነበረውን ሁኔታ ጠይቀን ለአንባቢዎቻችን እንደምናካፍል ቃል እንገባለን።

ያ’ገሬና የኔ –አትክልት አሰፋ (ጋዜጠኛ) –ከቫንኩቨር

$
0
0

እናቴና አገሬ ሙግት ገጠሙና፣
ሚስቴና እናት አለም ተወዳደሩና፣
ልጄ እና እማምዬ ፉክክር ገቡና፣
አንዱን ምረጥ ብለው ድርቅ ሲሉብኝ፤
እናቴም ውዴ ናት፣
ሚስቴም የኔ ፍቅር፤
ልጄም ንጉሴ ነው፤
የሚጣፍጥ ከማር፤
የግሌ የራሴ የማ’ለውጣቸው፣
በሰላሳ ዲናር የማልቀይራቸው፤
እናት፣ ሚስት፣ ልጄ፤ ሁሉም የኔ ናቸው።
እኔ ግን ያገሬ፤
እኔስ የ ‘ማምዬ…
የግል ንብረት ነኝ ብዬ መለስኳቸው።
ዲሴምበር 15/2013- ቫንኩቨር (በርናቢ)


በሕወሓት አፈና ቢፈተንም ዓረና መድረክ በማይጨው ሕዝባዊ ስብሰባ አደረገ

$
0
0

አብርሃ ደስታ ከመቀሌ

ባለፈው ቅዳሜ ዓረና መድረክ በጠራው ህዝባዊ ስብሰባ ለመሳተፍ ወደ ማይጨው ከተማ ተጉዤ ነበር። ከመቀሌ -ማይጨው በመኪና የሦስት ሰዓት ጉዞ ነው። ከሰባት ዓመት በፊት የማውቃት ማይጨው ምንም አልተቀየረችም። ብዙ የህወሓት ባለስልጣናት እዛው ማይጨው ነበሩ። ስብሰባዎችና ስልጠናዎች ነበሯቸው።

Arena-Tigray-logoቅዳሜ ከማይጨው ወጣቶች ጋር ተገናኝቼ ነበር። ወጣቶቹ ለውጥ ይፈልጋሉ። ግን ይፈራሉ። የሰለማዊ ትግል ዉጤታማነት ይጠራጠራሉ። ህወሓት በምርጫ ስልጣን ሊያስረክብ ይችላል ብለው አያምኑም። በሰለማዊ መንገድ ከሚቃወሙ በትጥቅ ትግል ቢሳተፉ ይመርጣሉ። ምክንያቱም በትጥቅ ትግል ህወሓት ከስልጣን የሚባረርበት ዕድል ሊኖር ይችላል ብለው ያስባሉ።

በማይጨው የሚገኙ የመንግስት ሰራተኞችም (በተለይ መምህራንና የግብርና ሰራተኞች) በስርዓቱ ቅሬታ አላቸው። የራያ አከባቢ ተወላጆች የሆኑ የህወሓት ካድሬዎችም በስርዓቱ ደስተኞች አይደሉም። ሁሉም ለውጥ ይፈልጋሉ። ግን ዓረና ህወሓትን ታግሎ ሊያሽንፈው ይችላል የሚል እምነት የላቸውም። በራያ ቦታ የሚገኙ የህወሓት አባላት (የራያ ተወላጆች) ህወሓትን ማሸነፍ የሚችል ተቃዋሚ ፓርቲ ካገኙ ህወሓትን እንደሚቃወሙ ይገልፃሉ።

የህወሓት መሪዎችም ይህንን ያውቃሉ። እንደዉጤቱም ህወሓት ከሌላ አከባቢ ታማኝ ካድሬዎች እየላከ የራሱ አባላት ይሰልላል፣ ይቀጣል፣ ያባርራል። በዚህ መንገድ የራያ ህዝብ በራሱ ሰዎች እንዲበደል ይደረጋል። የራያ ተወላጆች የሆኑ የመንግስት ሰራተኞች ለእንጀራቸው ሲሉ ህዝብ ይበድላሉ። ህዝብ ካልበደሉ ይቀጣሉ፣ ይባረራሉ፣ ሌላ የሚተዳደሩብት የስራ መስክ የላቸውም።

Abrham Destaየራያ ቦታ በህወሓት ከተረሱ አከባቢዎች አንዱ ነው። የራያ ህዝብ የክረምት ምግብ የነበረ ‘በለስ’ ለምርምር ተብሎ በገባ የሀር ትል ምክንያት ከጥቅም ዉጭ ሁነዋል። መንግስት የበለስ ጉዳቱ ለማካካስ የወሰደው እርምጃ የለም። በብዙ የራያ ቦታዎች የዉኃ ችግር አለ። የዉኃ ችግሩ ለመቅረፍ ብዙ ጉድጓዶች የተቆፈሩ ቢሆንም የዉኃ ቦይ ማስገባት ባለመቻሉ እስካሁን የዉኃ አገልግሎት የማያገኙ የራያ ቦታዎች አሉ።

ከዓመታት በፊት ለመስኖ እርሻ እንዲዉል በጥናት መሰረት የተመረጠ ‘የጎልጎል ራያ’ ሜዳም እስካሁን አልተተገበረም። የህወሓት መሪዎች ጎልጎል ራያን በመስኖ የማልማት ዕቅድ ሰርዘውታል። ፕሮጀክቱ ለመሰረዝ የሰጡት ምክንያት በራያ የሚገኝ ዉኃ ‘ጨዋማ’ ስለሆነ ለመስኖ ጥቅም አይውልም የሚል ነበር። የሚገርመው ነገር ደግሞ አሁን ጎልጎል ራያ በኢንቨስትመንት ስም ለባለ ሃብቶች እየተሸጠ ነው የሚገኘው። ስለዚህ የህወሓት ሰዎች የጎልጎል ራያን በመስኖ የማልማት ፕሮጀክት የሰረዙበት ምክንያት ሰፊ ለም መሬቱ ለባለሃብቶች ለመሸጥ ስለፈለጉ ሊሆን ይችላል።

የራያ ህዝብ ጀግናው ጥላሁን ይግዛውን ለመዘከር ሐውልት ለመገንባት ተብሎ ከራያ ተወላጆች ወደ 700,000 ብር የሚጠጋ ገንዘብ ከሰባት ዓመት በፊት የተሰበሰበ ሲሆን እስካሁን ድረስ ምንም ነገር አልተሰራም። የራያ ህዝብ ለጥላሁን ይግዛው ሐውልት ለመስራት የተሰበሰበ ገንዘብ የት እንዳለ ማወቅ ይፈልጋል፣ ይጠይቃል። አስተዳዳሪዎቹ የሰጡት መልስ ገንዘቡ ለኮብልስቶን አውለነዋል የሚል ነበር። ህዝቡም ኮብልስቶን የራሱ በጀት እንዳለው ሲከራከር ደግሞ አስተዳዳሪዎቹ ገንዘቡ የት እንዳለ እንደማያውቁ ይናገራሉ።

በማይጨው አከባቢ በሚገኙ ተቋማትም የሙስና አሰራሮች መኖራቸው ኗሪዎች ይናገራሉ። በዚሁ ምክንያት የችፑድ ፋብሪካ፣ ማይጨው ግብርና ኮሌጅና ማይጨው ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በተመሳሳይ ሁኔታና ወቅት የዳታ ኮምፒተሮች እንዲጠፉ ተደርገዋል። የዳታ ኮምፒተሮች እንዲጠፉ ሲደረግ ተቋማቱ ኦዲት እንዳይደረጉ ይረዳል። ኦዲት ካልተደረጉ ሙስና መሰራቱና አለመሰራቱ ለማወቅ ይከብዳል። የሙስና ጉዳይ ይፈተሽ።

ቅዳሜ ማይጨው በነበርኩበት ሰዓት በከተማው የኢንተርኔት አገልግሎት አልነበረም። ለዚህም ነበር ስለ ማይጨው ሁኔታ በወቅቱ መፃፍ ያልቻልኩ (ኢንተርኔት መጠቀም የሚቻለው በሞባይል ብቻ ነበር)። በወቅቱ የዓረና የማይጨው ከተማ አባላት የማይጨው ህዝብ ዓረና ፓርቲ በጠራው የእሁድ ህዝባዊ ስብሰባ እንዲሳተፍ ይቀሰቅሱ ነበር። ህዝቡም ለዓረና ጥሩ አመለካከት ነበረው። የዓረና አባላት ‘ዓረና’ የሚል ፅሑፍ ያለው ነጭ ቲ-ሸርት ለብሰው ነበር የሚቀሰቅሱ።

የህወሓት ሰዎችም ህዝብ በዓረና ስብሰባ እንዳይሳተፍ ለማድረግ የራሳቸው ቅስቀሳ ጀመሩ። ህወሓቶች ትልቅ ስፒከር ተጠቅመው በዕለተ እሁድ (በዓረና ስብሰባ) በማይጨው ከተማ የእግር ኳስ ውድድር ስላለ መላው ወጣት ተጫዋቾችን እንዲደግፍና እንዲያበራታታ ያውጁ ነበር።

የራያ ተወላጆች ያልሆኑ ካድሬዎች ለራያዎቹ በእሁድ ቀን በሚደረገው የዓረና ስብሰባ ሰው እንዳይሳተፍ እንዲመክሩና እንዲያስፈራሩ ተነገራቸው (ይህ መረጃ የተገኘው ከካድሬዎቹ ከራሳቸው ነው)። በስብሰባው የተሳተፈም እንዲመዘግቡ ትእዛዝ ተሰጣቸው። በተጨማሪም ሰው ለመያዝ ሲባል የተለያዩ ያልታሰቡ የህዝብ ስብሰባዎች ተጠሩ። አብዛኛው የማይጨው ወጣት በራሳቸው ስብሰባ እንዲገኝ አዘዙት። የችኮማዮና የመኾኒ ‘ስራ አጥ’ ወጣቶች ‘ስራ እንዲሰጣቸው’ ለእሁድ ስብሰባ ተጠሩ። እሁድ በስብሰባው የተገኘ ስራ እንደሚሰጠው፣ ያልተገኘ ግን ስራ እንደማያገኝ ተነገረው።

የማይጨው ህዝብም ለህወሓት ታሪክ ለመጀመርያ ግዜ የሙዚቃ ባንድ እንደሚመጣለት ሲነገረው ነበር። ህወሓት በማይጨው ከተማ የሙዚቃ ኮንሰርት ሲያዘጋጅ (ወይ አዘጋጃለሁ ሲል) ለመጀመርያ ግዜ ነው። ይህም ዓረና ህዝባዊ ስብሰባ በጠራበት ቀን ነው። እሁድ ቀን በስብሰባው ተሳታፊ ስለነበርን ህወሓቶች የራሳቸው ስብሰባ ስለማካሄዳቸው ሙሉ መረጃ አልነበረኝም። የሙዚቃ ኮንሰርቱ ስለ መሳካቱም እርግጠኛ አይደለሁም። የሙዚቃ ኮንሰርቱ ያልታቀደና ያልታሰበበት ስለነበረ ያልተሳካ ሙከራ ሊሆን ይችላል (ከተጋበዙት ሙዚቀኞች ቅሬታ ያሰሙ ነበሩ፤ በቂ ግዜ ስላልተሰጣቸው)።

እሁድ ጠዋት ሰው ዓረና ወደ ጠራው ስብሰባ መግባት ከመጀመሩ በፊት የተወሰኑ የፀጥታና የፕሮፓጋንዳ ሐላፊዎች አደራሹ አከባቢ ተሰብስበው ነበር። ወደነሱ አከባቢ ስንሄድ ተበትነው ጠፉ። አብዛኞቹ የማይጨው ካድሬዎችና ፖሊሶች ግን ተባብረውናል። ተሳታፊ እንዲሰልሉና እንዲያስፈራሩ የተላኩ ካድሬዎች ከጎናችን ነበሩ። ‘እንደምንም ብላቹ ህወሓትን ማባረር የምትችሉ ከሆነ ከጎናቹ ነን’ ይሉን ነበር። ላደረጉልን ትብብር እናመሰግናለን። ህወሓትን ከስልጣን ማባረር የምንችል ግን ሁላችን ስንተባበር ነው።

ህዝብ ወደ አደራሹ ገባ። ስብሰባውም ተጀመረ። እኛ ስለ ህወሓት መጥፎነትና የለውጥ አስፈላጊነት አወራን። ህዝቡም አስተያየት ሰጠ። ከህዝቡ የተረዳነው ነገር ቢኖር የራያ ህዝብ የህወሓትን መጥፎነት ከኛ በላይ ያውቃል። የህዝቡ ጥያቄ ህወሓትን እንዴት ከስልጣን ማውረድ ይቻላል? ዓረናስ አንዴ እየመጣ፣ ብዙ ግዜ እየጠፋ ህወሓትን ማሸነፍ ይችላል ወይ? ዓረናን ብንደግፍና ህወሓትን ከስልጣን ማባረር ባንችል ዋስትናችን ምንድነው? ህወሓት ሽፍታ ነው፤ ሊያጠፋን ይችላል ወዘተ የሚሉ ሐሳቦች ተነስተዋል።

ህዝቡ በሰጠው አስተያየትና ትንተና ተገርምያለሁ። ህዝቡ ለውጥ ይፈልጋል። በህወሓት መሪነት እምነት የለውም። ህዝቡ ያጣው ነገር ህወሓትን ሊያባርር የሚችል ዓቅም ያለው የተቃዋሚ ፓርቲን ነው። ህዝቡ የሚመራው ፓርቲ ካገኘ ለመታገል ዝግጁ ነው። ዓረና ቆራጥነት ካለው ህዝቡ ከዓረና ጎን ተሰልፎ እንደሚታገል ቃል ገብተዋል።

የማይጨው ስብሰባ ለየት የሚያደርገው ተሰብሳቢው በሙሉ የህወሓት ተቃዋሚ መሆኑ ነው። የህወሓት ካድሬዎች አልነበሩም። ሁላችን በአንድነት ለመታገል ቃል ስንገባ በአደራሹ የነበረ ሁሉ ቃሉ ሰጠ። አብረን ለመታገል ቃል ገባን። (ኩልና ብሓባር ንምቅላስ ንዓሪ ኢልና ዓረና)። ሦስት ሰዓት ተኩል የጀመረ ስብሰባችን ዘጠኝ ሰዓት ተኩል ተጠናቀቀ።

እኔ የተረዳሁት ነገር አለ። የህወሓት ስጋት ዓረና አይደለም። የህወሓት ስጋት የህዝብ ማወቅ ነው። ህወሓት የትግራይ ህዝብ የፖለቲካ እውቀት እንዲኖረው አይፈልግም። ምክንያቱም የትግራይ ህዝብ የፖለቲካ ንቃተ ህሊናው ከፍ ካደረገ ለህወሓት ካድሬዎች አሜን ብሎ አይገዛም። ካልተገዛ ደግሞ የህወሓቶች ህልውና ያበቃል። የህወሓቶች ጥረት ህዝብ በስብሰባው እንዳይሳተፍና አማራጭ ሐሳብ እንዳይሰማ መከልከል ነበር። ህወሓት የሚሰጋው ዓረና እንዳይቃወመው ሳይሆን ህዝቡ ፖለቲካ አውቆ እንዳይቃወመው ነው።

ይሄ ተንኮል ግን የህወሓት ዕድሜ ያራዝማል የሚል ግምት የለኝም።

በ“ኢትዮጵያ ጋዜጠኞች መድረክ” መስራች ኮሚቴ የተሰጠ መግለጫ

$
0
0

መስራች ጊዜያዊ ኮሚቴ  
ታህሳስ 3 ቀን 2006 ዓ.ም

newspaper_for_rentበሀገራችን ሀሳብን በነፃነት የመግለፅ መብት ተረጋግጧል ከተባለበት ከ1985ዓ.ም. ጀምሮ የመገናኛ ብዙሃን ሙያ ከመጎልበት ይልቅ እያደር በመጫጨት ላይ ይገኛል፡፡ ከዚህም ጋር በተያያዘ  የሙያው ባለቤቶች የሆኑት ጋዜጠኞች ለተለያዩ ጥቃቶች ሲጋለጡ ቆይተዋል፡፡ ለምሳሌ ጋዜጠኞች በስራቸው ምክንያት አለአግባብ ይታሰራሉ፤ ማስፈራሪያና ዛቻ ይደርስባቸዋል፣ ይደበደባሉ፣ ማግኘት የሚገባቸውን ጥቅማ ጥቅሞች እና መብቶቻቸውን ይነፈጋሉ፣ ሲልም ከዚህ የከፉ በደሎች ይደርሱባቸዋል፡፡ የሚያሳዝነው ደግሞ ከመንግሥት ከሚደርስባቸው መሰል የመብት ጥሰትና እንግልት በተጨማሪ፣ ለራሳቸው ጥቅም ሲሉ መገናኛ ብዙሃንን መመዝበር የሚፈልጉ የተለያዩ አካላትም ጥቃት ሰለባ መሆናቸው ይታወቃል፡፡ ከዚህም ባሻገር በተለያየ መንገድ ጥቅሞቻቸው አይከበሩም፡፡

ይህ በእንዲህ እንዳለ፣ ጋዜጠኞች ለሌሎች መብት መከበር የሚጮሁትን ያህል በራሳቸውና በሙያው ላይ የተጋረጡ ተግዳሮቶችን በጋራ ለመፍታትም ሆነ እንዳይፈጠሩ ለመስራት አልታደሉም፡፡ ይህንን ሊያከናውን የሚችል ተቋምም ሆነ ማህበር የላቸውም ለማለት ይቻላል፡፡ ለምሳሌ በቅርቡ በኢትዮ-ምኅዳር ከፍተኛ አዘጋጅ ኤፍሬም በየነ ላይ የደረሰውን ሁሉ መመልከት ይቻላል፡፡ ጋዜጠኛው የሥራ ባልደረቦቹ የቀረበባቸውን ክስ ለመከላከል እና እግር መንገዱን የሙያ ግዴታውን ለመወጣት በሄደበት ወቅት የደረሰበትን አወዛጋቢ የትራፊክ አደጋ ተከትሎ በተግባር ለጋዜጠኝነትና ለጋዜጠኞች የሚቆረቆሩ ተቋማት አለመኖራቸው በተጨባጭ የታየ ጉዳይ ነው፡፡ ስለሆነም እነዚህና መሰል ችግሮች በእርግጥም ነፃና ገለልተኛ የሆነና ለጋዜጠኝነት ሙያ እንዲሁም ለጋዜጠኞች መብት የቆመ ማኅበር ማቋቋም ጊዜ የማይሰጠው ጉዳይ አድርጎታል፡፡

ከዚህ እውነት በመነሳት ከጥቅምት ወር 2006 ዓም ጀምሮ “የኢትዮጵያ ጋዜጠኞች መድረክ” በሚል ስያሜ በጋዜጠኝት መርህ ላይ የተመሰረተ እና ለጋዜጠኞች መብት የቆመ የሙያ ማኅበር ለመመስረት ሰፊ ጥረት እየተደረገ ይገኛል፡፡ የሙያው ባለቤቶችም በጋራ ተባብረው ማኅበሩን በቅርቡ እውን ያደርጋሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡ ይህንንም ጋዜጣዊ መግለጫ ማዘጋጀት ያስፈለገው ይህንን የተግባር እንቅስቃሴ ይፋ ለማድረግ ነው፡፡

“የኢትዮጵያ ጋዜጠኞች መድረክ” የሚመሰረተው በሕገ-መንግስቱ አንቀፅ 30 በተፈቀደው የመደራጀት መብት መሠረት ሲሆን፣ በአጠቃላይ ጋዜጠኞችን በመደገፍ፣ የሙያ ብቃታቸውን በማሻሻል እንዲሁም በማበረታታት በሀገሪቱ ያለውን የጋዜጠኝነት ሙያ ለማበልፀግ የሚሰራ ነፃ የሙያ ማኅበር ይሆናል፡፡ ምንም እንኳን ማኅበሩ በርካታ ዝርዝር ዓላማዎችን ያነገበ ቢሆንም፣ በዋናነት ተጠቃሾቹ የሚከተሉት ናቸዉ፡-

1. በኢፌድሪ ሕገ- መንግሥት አንቀፅ 29 መሠረት የተፈቀደውን ሀሳብን በነፃነት የመግለፅ መብት ለማስከበር

2. የጋዜጠኞችን መብትና ጥቅም ለማስጠበቅ

3. በተከታታይ ትምህርትና ሥልጠና የጋዜጠኞችን ሙያዊ ብቃት ለማጎልበት

4. በጋዜጠኞች መካከል ያለውን ግንኙነት ለማጠናከር

5. አስፈላጊ ሆኖ በተገኘ ጊዜ የገንዘብ፣ የቁሳቁስና የሕግ አገልግሎት ድጋፍ ለማደረግ

6. በዘርፉ አስተዋፅኦ ላበረከቱ ጋዜጠኞች እውቅና ለመስጠት የሚሉ ናቸው፡፡

የኢትዮጵያ ጋዜጠኞች መድረክ በዋናነት በአባልነት የሚያቅፋቸው አባላት በጋዜጠኝነት ሙያ በማንኛውም የመገናኛ ብዙሃን መስክ አገልግሎት በመስጠት ላይ የሚገኙትን ሲሆን፤ ከዚህም በተጨማሪ በሙያው ለመሰማራት በሂደት ላይ የሚገኙትንና ከሙያው ጋር ከፍተኛ ቁርኝት ያላቸውን ግለሰቦች ተባባሪ በሚል የአባልነት ዘርፍ ያቅፋል፡፡

ስለሆነም በሙያው አገልግሎት በመስጠት ላይ የምትገኙ ጋዜጠኞች ሁሉ፣ በዚህ በምስረታ ላይ ባለው የእናንተው ማኅበር ላይ፣ የበኩላችሁን ንቁ ተሳትፎ በማድረግ የማኅበሩን ህላዌ እውን ታደርጉ ዘንድ ተጋብዛችኋል፡፡ በቅርቡም በሚጠራው ጠቅላላ ጉባዔ ላይ የነቃ ተሳትፎ በማድረግ፣ የማኅበሩን የአመራር አባላት በመምረጥ ሂደት እንድትሳተፉ ጥሪ እናቀርባለን፡፡

 

እናመሰግናለን!!!

መስራች ጊዜያዊ ኮሚቴ  

 

ታህሳስ 3 ቀን 2006 ዓ.ም

 

 

 

 

 

Hiber Radio: ከሳዑዲ የመጡ ኢትዮጵያውያን ባለባቸው ችግር የተነሳ ተመልሰው ለመሰደድ ማሰባቸውን ገለጹ

$
0
0

የህብር ሬዲዮ ታህሳስ 6 ቀን 2006 ፕሮግራም

ጋዜጠኛ ሃብታሙ አሰፋ

ጋዜጠኛ ሃብታሙ አሰፋ

>

አቶ ኪዳኔ አለማየሁ የዓለም አቀፍ ህብረት ለፍትሕ የኢትዮጵያ ጉዳይ ዋና ስራ አስኪያጅ ለህብር ከሰጡት ቃለ መጠይቅ

> አቶ ሳሙኤል አለባቸው በእስራኤል የኢትዮጵያን እናድን ማህበር ሊቀ መንበር በዚያ ስላለው የኢትዮጵያውያን ስደተኞች ጉዳይ ከደረግነው ወቅታዊ ቃለ መጠይቅ የተወሰደ

ማንዴላ ማንዴላ(ግጥም)

ታይም መጽሔት የዓለማችን ሰው ስላላቸው የካቶሊኩ ጳጳስ የተጠናከረ ዘገባ

ሻምበል ጉታ ዲንቃ(የማንዴላን ህይወት ከተቀነባበረው የግድያ ሙከራ የታደጉት ሰው በማንዴላ ቀብር ላይ እንዲገኙ ወደ ደቡብ አፍሪካ እንዲሄዱ የተደረገበትን ሁኔታ በተመለከተ ቃለ መጠይቅ

ኩላሊት ምን ሲሆን ስራውን ያቆማል ? አስቀድሞ መከላከል ይቻላል? (የህክምና ባለሙያ ማብራሪያ)

ሌሎችም ዝግጅቶች

ዜናዎቻችን

- የማንዴላ ስርዓተ ቀብር በታላቅ ስርዓት ተከናወነ

- ከሳውዲ የመጡ ኢትዮጵያውያን ባለባቸው ችግር ተመልሰው ለመሰደድ ማሰባቸውን ገለጹ

- የአጼ ምንሊክ መቶኛ ዓመት መታሰቢያ በዓለም አቀፍ ደረጃ ሊከበር እንደሚገባ ተገለጸ

- በኢትዮጵያ ከአስር ዓመት በፊት የተደረገው ጭፍጨፋ ታሰበ

- በቬጋስ የሚገኝ ቤተ ክርስቲያን ለህንጻ ማሰሪያ በአንድ ምሽት 322 ሺህ ዶላር ተሰበሰበ

ሌሎችም ዜናዎች አሉን

10ሩ የማንዴላ ድንቅ አባባሎች (ፍኖተ ነፃነት ቁጥር 82)

$
0
0

Fnote910ሩ የማንዴላ ድንቅ አባባሎች
ያልተመለሰው የመሬት ጥያቄ
ቀናዋ የማንዴላ መንገድ
የማይበቅል ዘር በመሰራጨቱ
በገበሬዎችና በባለስልጣናት
ማሀከል ውጥረት ተፈጠረ
በጉጂ ዞን መንግስታዊ
ስርዓት አልበኝነት ተባብሷል
ፍኖተ ነፃነት ቁጥር 82 ሰኞ ታህሳስ 7 ቀን 2006 ዓ.ም

–ፍኖተ ነፃነት ቁጥር  - 82 _PDF_

 

አይ አበሻ! አበሻና ልመና፦ አንድ (መስፍን ወልደ-ማርያም)

$
0
0

መስፍን ወልደ ማርያም

ኅዳር 2006

Pro Mesfinበዓለም ሕዝቦች መሀከል ውድድር ቢደረግ ያለጥርጥር አበሻ አንደኛ ከሚወጣባቸው ነገሮች አንዱ ልመና ሳይሆን አይቀርም፤ ለአበሻ፣ ልመና የኑሮ ዘዴ ነው፤ እንዲያውም ከልመና ውጭ የሆነ ኢትዮጵያዊ ኑሮ የለም ለማለት የሚቻል ይመስለኛል፤ ስለዚህም ልመና ባህላዊ ጥበብ ሆኖአል፤ አንዳንድ አላዋቂዎች፣ አንዳንድ አዋቂዎችም አንዳንዴ እየተሳሳቱ ልመናን እንደነውር ይገልጹታል፤ ልመና ነውር አይደለም፤ ለጨዋ ልጆችማ አንዳንድ አጥንትን የሚያበላሽ ሥራ ከመሥራት ለምኖ መብላት ክብር ነው፤ ይህ ባህላዊ ጥበብ ያልገባቸው የድሬ ዳዋ ለማኞች ብቻ ናቸው፤ እጃቸውን እየዘረጉ ‹‹እስቲ አሥር ብር ስጠኝ!›› ይላሉ! በጫት ሞቅ ሲላቸው መቶ ብር ይጠይቃሉ፤ የድሬ ዳዋ ልመና መሆኑ ነው!

የጥበብ መጀመሪያ እግዚአብሔርን መፍራት ነው፤ ቄሶቹ ምንም ይስበኩ በተግባር እንደሚታየው ጽድቅ የሚገኘው በልመና ነው እንጂ በሥራ አይደለም፤ ሥራኮ ለአበሻ ከእርግማን የመጣ ነው፤ አበሻ አልተረገመ፤ ታዲያ ለምን ብሎ ይሥራ! አሁን እንደሚሰማውና እንደሚመስለኝ አገዛዙም እንደተቀበለው የቻይና ሰዎችም እንደመሰከሩለት ከሥራ ጋር ጠብ አለው፤ ደግሞስ ለምን ይሥራ! ለአንድ እንጀራ? ለተራበ አብልተው ለመጽደቅ የሚፈልጉ ስንትና ስንት ሰዎች አሉ፤ ስለዚህም ደግ ሰዎች መጽውተው እንዲጸድቁ በግድ ለማኞች ያስፈልጋሉ፤ ለመጽደቅም መለመን ያስፈልጋል፤ ጸሎት ልመና መሆኑን አትርሱ፤ ስለዚህም ዋናውና ከፍተኛው ልመና ወደእግዚአብሔር ነው፤ ብልጦቹ እግዚአብሔርን የሚለምኑት ሥልጣን፣ ሀብትና ጉልበት ነው፤ አንድ ቀን ተነሥተው እግዚአብሔር ሥልጣን፣ ሀብትና ጉልበት እንደሰጣቸው ያውጃሉ፤ አውጀውም በሕዝብ ራስ ላይ ይወጣሉ፤ በራሱ ላይ ወጥተውም ይጨፍራሉ፤ ሰውን ከመሬቱ፣ መሬቱን ከሰው መለየት ይሳናቸዋል፤ ሰውን ከመሬቱ፣ መሬቱን ከሰው ያጣላሉ፤ እግዚአብሔር ለእናንተ ብቻ እንዴት ሰጣችሁ? እግዚአብሔር እኛን ለምን ነፈገን? ብሎ የሚጠይቃቸውን እየደበደቡና እያቃጠሉ፣ እየገረፉና እያራቆቱ በዝምታ እንዲገዛ ያደርጉታል፤ አልበቃው ካለም አካሉን ለውሻ ሰጥተው ነፍሱን ወደእግዚአብሔር ይወረውራሉ፤ እግዚአብሔር እየቆጠረ የማይመዘግብ ይመስላቸዋል፤ የጠጠረ ጉልበታቸው ዓይኖቻቸውን አውሮ፣ ኅሊናቸውን አፍኖ እግዚአብሔር በዕዳ እንደሚይዛቸውና በጥጋባቸው ያደሉትን መከራና ስቃይ፣ የወረደውን እንባና ደም ከነወለዱ እንደሚያስከፍላቸው መገንዘብ ያቅታቸዋል።

እግዚአብሔር ፍርዱን እስቲሰጥ ድረስ ሥልጣን፣ ሀብትና ጉልበት ተረክበናል የሚሉት የተለያዩ ስሞችን እየለጠፉ በተዋረድ የለማኞችን ሠራዊት ያደራጃሉ፤ ሕዝብ ሁሉ ከነዚህ የለማኞች ሠራዊት በአንዱ ውስጥ ለመግባት በፉክክር ይተላለቃል፤ ሠራዊቱ ውስጥ በመግባት የሚገኘው ጉርሻ ልጆቻቸውን እንኳን ከረሀብ የማያድን መሆኑን ሳይገነዘቡ መብታቸውን እያስረገጡ የሌሎችን መብት ለመርገጥ መሣሪያ ይሆናሉ፤ እነዚህ እንግዲህ ልመናን በማኅበረሰቡ ውስጥ ተክለው እየኮተኮቱ የሚያስፋፉት ናቸው፤ ልመናን ባህል የሚያደርጉት እነዚህ ናቸው፤ ልመናን ታሪካችን ያደረጉት እነዚህና ከነሱ የቀደሙት ገዢዎቻችን ናቸው።

በእኛ ባህል የራበውን በማብላት ጽድቅ ይገኛል፤ ስለዚህም ለምኖ መብላት ይቻላል፤ ስለዚህም ሰዎች መጽውተው እንዲጸድቁ በግድ ለማኞች ያስፈልጋሉ፤ እንግዲህ ለምነው እየበሉ መኖር ከተቻለና እግዚአብሔርን በመለመን ጽድቅ ከተገኘ፣ የመሬቱንና የሰማዩን ጣጣ በልመና መገላገል ከተቻለ ታዲያ ሥራ ለምን ያስፈልጋል! ለነገሩስ ሥራ በእርግማን የመጣ ነው፤ ስለዚህ የተረገሙት ሲሠሩ ያልተረገሙ የሚመስላቸው ይለምኑ፤ ለሌላው ዓለም ልመና የችግር ምልክት ነው፤ ለአበሻ ግን ልመና የጽድቅ ምልክት ነው፤ የጨዋ ልጅ፣ ማለት በልመና በሰዎች ላይ ሥልጣንን ከአግዚአብሔር አግኝቻለሁ ብሎ የሚያምን፣ አይሠራም፤ ቀን ቢጥለውም የጨዋ ልጅ በእጁ ሠርቶ ከሚበላ ለምኖ ቢበላ ይሻለዋል፤ ሆድ የተፈጥሮ ነው፤ ረሀብም የዕለት ከዕለት የተፈጥሮ ግዳጅ ነው፤ ስለዚህም ለአበሻ የተፈጥሮን ሆድና የተፈጥሮን ረሀብ በልመና መወጣት የተፈጥሮን ሥርዓት መከተል መስሎ ይታየዋል።

ሌላ ቀርቶ ተማሪ ለምኖ ካልበላ ትምህርት አይገባውም፤ ለተማሪ ሲሆን ልመና አይባልም፤ ቀፈፋ ነው፤ አበሻ በልመና ምን ይህል እንደተራቀቀ የሚያመለክተው ለተለያዩ ልመናዎች የተለያዩ ስሞች ማውጣቱ ነው፤ እንደተባለው ተማሪ ሲለምን ቀፈፋ ነው፤ በዘመናዊ ቋንቋ የትምህርት ታክስ ነው፤ ምግብ የሚቀርብበትን ሰዓት እየጠበቀ ከተፍ የሚለው ቀላዋጭ ነው፤ አብዛኛውን ጊዜ ለቀላዋጭ ቀላል ሰበብ የሚሆነው ቀላውጦ የሚያገኘው ወሬ ነው፤ ሌላም የልመና ዓይነት አለ፤ እርጥባን ይባላል፤ — ደርቄአለሁና አርጥቡኝ ማለት ነው! ‹ላሊበላዎች› የሚባሉት ለምነን ካልበላን እንቆመጣለን በማለት ልመናን የኑሮ መሠረት አድርገውታል፤ ሌላም የልመና ዘር አለ፤ ደጅ መጥናት ይባላል፤ ደጅ መጥናት ማለት ብርዱን ችሎና እንቅልፉን አቋርጦ በሌሊት እየተነሡ በመኳንንቱና በመሳፍንቱ፣ በንጉሡ፣ በንጉሠ ነገሥቱ ደጃፍ ላይ አጥር ወይም ዛፍ እየተደገፉ የተፈለገውም ሰው ብቅ ሲል በመሬት ላይ በመነጠፍ እጅ በመንሣት ፊት ለማስወጋት ለመታወቅና ለሹመት ለመታጨት የሚጠቅም የልመና ዘዴ ነው፡፡ በአበሻ አገር ሁሉም ነገር በልመና ነው፤ ምግብ በልመና፣ ትምህርት በልመና፣ መሬት በልመና፣ … በልመና፣ ግብር የሚከፈለው በልመና ነው፤ ሥልጣን የሚገኘው በልመና ነው፤ ንጉሥነትም የሚገኘው በልመና ነው፤ ባጭሩ ኑሮ ማለት ልመና ነው፤ ልመና ማለት ኑሮ ነው ።

 

 

Viewing all 15006 articles
Browse latest View live


<script src="https://jsc.adskeeper.com/r/s/rssing.com.1596347.js" async> </script>
<script src="https://jsc.adskeeper.com/r/s/rssing.com.1596344.js" async> </script>