Quantcast
Channel: Ethiopian News | ዘ-ሐበሻ | Latest News Provider | News For All
Viewing all 15006 articles
Browse latest View live

ከመቶ አመት የቤት ስራወቻችን አንዱ የሆነው የኦነግ አፍራሽ ተልእኰ (ከይገርማል)

0
0

Ethiopiaሕዝቡ ከዳር እስከዳር በምሬት ተነስቶ በወያኔ ላይ የሚሰነዝረውን ጡጫ እያበረታ ነው:: ወያኔም በበኩሉ “ተመጣጣኝ ርምጃ” በሚለው ጥቃት በርካታ ዜጎችን ተኩሶ እየጣለ ነው:: ለአመታት ተደክሞ በብዙ ወጪ የተገነቡ ፋብሪካወችና ድርጅቶች በአንድ ቀን እሳት እንዳልነበሩ እየሆነ ነው::  ልቡ በክፋት ለተደፈነው ወያኔ ይህ ሁሉ የሚያሳስበው አይመስልም:: እንዲያውም አለመረጋጋቱን አጥብቆ የሚፈልገው ይመስላል:: የወያኔ አውራወች ችግሩን የሚያባብስ ርምጃ ሲወስዱ እንጅ መፍትሄ ለመፈለግ ሲሰሩ አይታዩም:: እንቅስቃሴው የፈጠረው አንድ በጎ ነገር ቢኖር ወዲያና ወዲህ ሆነው በጠላትነት እንዲተያዩና እንዲጠፋፉ ሸር ሲጎነጎንባቸው የነበሩ ጎሳወች ልዩነታቸውን አጥብበው: ጥላቻቸውን ፍቀው በአንድነት መሰለፋቸው ነው:: ለብዙ አመታት ፊት ተዟዙረው የነበሩት ስልጤወችና ጉራጌወች ይቅር ተባብለዋል:: በጥርጣሬ ይተያዩ የነበሩት ኦሮሞወችና አማራወች “በወያኔ ተንኮል ነቅተናል!” ብለው እጅ ለእጅ ተያይዘው በአንድነት ቆመዋል:: ይሁን እንጅ የወያኔ ቅጅ የሆነው ኦነግ (በስም ብዙ በባህርይ ግን አንድ የሆኑ የኦሮሞ ድርጅቶች) የሚባለው ድርጅት ሰዎች ይህን የሕዝቦች አንድነት አጥፍተው በምትኩ ክፍፍልን እና ጥላቻን ለመትከል ከፍተኛ ደባ እየፈጸሙ ነው::

አቶ ጃዋር መሀመድ ሰሞኑን የተናገረው ነገር በጣም የሚረብሽ ነው:: ይህን ሰው ባልተገራ አንደበቱ ምክንያት ብዙወች ይንቁታል::  የሚናገራቸው ነገሮች የተቀመጠበትን የሀላፊነት ቦታም ሆነ የአንድ ጤነኛ ሰው ባህሪን የሚመጥኑ እንዳልሆነ ነው የሚነገረው:: ጃዋር የክርስቲያኖቹን አንገት ለሜንጫ ከተመኘ ጀምሮ በብዙወች ዘንድ ጥላቻን ያተረፈ ሰው ሆኗል:: ይህ ሰው የፖለቲካ ድርጅት አባል እንዳልሆነ ይናገራል:: ይሁን እንጅ የሚያራምደው ሀሳብ ያለጥርጥር ደም ከጠማቸው የኦነግ አባላት ውስጥ አንዱ መሆኑን የሚያረጋግጥ ነው::

ኦነግ የወያኔን እና የሻእቢያን እቅድ ለማስፈጸም በመቆም እጅግ ብዙ አማራውችን በአሰቃቂ ሁኔታ የገደለ ሀላፊነት የማይሰማው አሸባሪ ድርጅት ነው:: በንጹሀን አማሮች ላይ የተፈጸመውን  ጭፍጨፋ መቸም ቢሆን ታሪክ  የሚዘነጋው አይሆንም:: አማራወች በኦሮሞወች ላይ ከ120 አመት በፊት ፈጽመውታል በተባለው በሬ-ወለድ ጭፍጨፋ መነሻ በዚህ በሰለጠነ ዘመን የአሁኑን አማሮች በበቀል የፈጀ እጅግ የተበላሸ ኋላቀር ድርጅት ነው:: ይህ በሻእቢያ እገዛና ኢትዮጵያን እንደሀገር ማየት በማይፈልጉ ሀይሎች የተቋቋመው ድርጅት የሀገራችንን ታሪክ ለማበላሸት እና አንድነቷን አደጋ ላይ ለመጣል እረፍት አጥቶ ግፍ ሲፈጽም ኖሯል:: ለኤርትራ መገንጠል: ለኢትዮጵያ ታሪክ መጉደፍ: በኢትዮጵያውያን መሀል ልዩነት እና ጥላቻ ስር መስደድ: ለአማሮች መጨፍጨፍ እና ሀገራችን ለጥቃት ተጋላጭ እንድትሆን በማድረግ በኩል ጉልህ ድርሻ አበርክቷል:: ኦነግ ዛሬም እንኳ ከጥፋቱ ሊመለስ የማይፈቅድ ድርጅት መሆኑን በአቶ ጃዋር በኩል አስረግጦ እየነገረን ነው::

 

አቶ ጃዋር የፖለቲካን ሀ – ሁ ሳይረዳ የፖለቲካ ተንታኝ እና አክቲቭስት የሚል ስም የተሰጠው አፉ እንዳመጣ የሚናገር  ያልበሰለ ሰው እንደሆነ ብዙወች ይስማማሉ:: ለነገሩ ኦነግ ውስጥ ምራቁን የዋጠ አስተዋይ ሰው ማግኘት ከባድ ሳይሆን አይቀርም:: አቶ ጃዋር ስለኦሮሚያ የሽግግር ጊዜ ሰነድ ሲያወራ: ስለኦሮሚያ ከፖለቲካ ነጻ የሆነ የጦር ሰራዊት ምስረታ ደረቱን ነፍቶ ሲናገር የኦሮሚያን ነጻ ሀገር አይቀሬነት እያረጋገጠልን መሆኑ ነው:: ይህ ግለሰብ የኦነግን ትንፋሽ ሳይይዝ በራሱ ጊዜ ፈጥሮ ያወራል ማለት አይቻልም:: ኦነግ አሁንም የኢትዮጵያን ሕዝብ መጠፋፋት እያወጀልን ነው:: በሰላምና በፍቅር አብሮ የኖረውን የኢትዮጵያ ሕዝብ በሸር ለያይቶ በመሬት ይገባኛል ጥያቄ እርስ በርስ ሊያጫርስ በጽናት ቆሟል:: አቶ ጃዋር የተናገረው ነገር በተሳሳተ መልኩ እንደተተረጎመ አድርጎ በዘሀበሻ ላይ ጽፎ ያስነበበን ጽሁፍ ያንኑ የኦነግን አላማ በድጋሚ የሚያረጋግጥ ነበር:: ደስ ሲላቸው የብሔር-ብሔረሰቦች መብት የሚከበርባት ዴሞክራሲያዊት ኢትዮጵያን በጋራ መስርተን በአንድነት እንኖራለን የሚሉት ኦነጎች ብዙም ሳይቆዩ ‘በኢትዮጵያ ውስጥ እንቀጥል ወይስ የራሳችን ሀገር እንመስርት?’ በሚለው ጉዳይ ላይ የኦሮሞ ሕዝብ ብቻ ነው ሊወስን የሚችለው ብለው እውነተኛ ፍላጎታቸውን ያወጡታል:: አቶ ጃዋር ስለመከላከያ ሰራዊት ምስረታ ሲያወራ ምን ለማለት እንደፈለገ የማይገነዘብ ሰው አይኖርም:: በክልል ወይም በክ/ሀገር ወይም በአካባቢ በአንዲት ፌደራላዊት ሀገር ውስጥ ከሌሎች ጋር አብሮ የሚኖር ሕዝብ የአካባቢ ፖሊስ እንጅ መከላከያ ሰራዊት ሊኖረው አይችልም:: መከላከያ ሰራዊት የሀገሪቱን ሉአላዊነት ለማስጠበቅ በሀገር ደረጃ የሚቋቋም ወታደራዊ ሀይል ነው::

 

የ1997 ዓ.ም ሀገር አቀፍ እና ክልላዊ ምርጫን ተከትሎ ቅንጅት አሸንፏል ብለው ያመኑት የተቃዋሚ ኃይሎች ሕብረት አመራሮች ለዴሞክራሲያዊ ስርአት የሚታገሉ መሆኑን እረስተው በምርጫ ውድድር ያሸነፈው ቅንጅት ላይ ዘምተው እንደነበር የሚረሳ አይደለም:: በውድድር ያሸነፈውን ስልጣን ትቶ ሁሉንም የሚጋብዝ የሽግግር መንግሥት እንዲመሰረት በቅንጅት ላይ ጫና ሲያደርጉ የነበሩት ተቃዋሚወች ፍላጐታቸው የተከፈተው የሰላማዊ እና የዴሞክራሲያዊ የስልጣን ሽግግር ስርአት እውን በመሆኑ ተደስተው ዴሞክራሲያዊ ስርአቱ እንቅፋት እንዳይገጥመው በመከላከል ወደተሻለ የእድገት ደረጃ እንዲሸጋገር ለማገዝ ሳይሆን ስልጣን ለመጋራት ነበር:: ማንም ይሁን ማን በሕዝብ እስከተመረጠ ድረስ የሕዝብን ውሳኔ አክብሮ መቀበል የዴሞክራሲያዊ ስርአቱ አንድ መገለጫ መሆኑን ረስተው በሕዝብ ፈቃድ የተመረጠው ቅንጅት ላይ የጥላቻ እና የምቀኝነት ዘመቻ ሲያካሂዱ ወያኔን ጭራሽ እንደሞተ ቆጥረውት ነበር:: ከዚህ ሁሉ በኋላ ሞቷል ተብሎ የታሰበው ወያኔ በራሱ መንገድ ተጉዞ ሁሉንም በሚፈልገው መልክ ሲያስተካክል ተቃዋሚ ድርጅቶች ከርስ በርስ ንክሻ ወጥተው እንደለመዱት በየፊናቸው በወያኔ ላይ መጮህ ጀመሩ::

የዛሬው የኦነግ የጦር ሰራዊት ምስረታ ዕቅድ የመነጨውም ወያኔ እየሞተ ነው ከሚለው የተሳሳተ ስሌት የተነሳ ነው:: አሁን በየአካባቢው እየተደረገ ያለው አመጽ የወያኔን ቀብር አቅርቦታል ብለው ያመኑት ኦነጎች እውነተኛውን ፍላጎታቸውን አውጥተው ኦሮሚያን ብቻ የሚመለከት የሽግግር መንግስት ምስረታ ሰነድ ለማዘጋጀት እና የመከላከያ ሰራዊት ለመገንባት እየተዘጋጁ እንደሆነ እየነገሩን ነው:: ይህ አካሄዳቸው ትግሉን ምን ያህል ሊጎዳው እንደሚችል የተገነዘቡት አይመስልም:: በመጀመሪያ ደረጃ ወያኔ እነርሱ እንደሚያስቡት ሊሞት በጣዕር ላይ ያለ ድርጅት አይደለም:: ሌላው ደግሞ ወያኔ ‘ጉድጓዱ የተማሰ ልጡ የተራሰ’ ነው ብለን ብናስብ እንኳ የኦሮሚያ መንግስት ምስረታ ሀሳብ ለሁሉም ኢትዮጵያዊ ዘላቂ ሰላም የሚያመጣ ፍቱን መፍትሄ አይደለም::

 

በየጊዜው እንደምናየው በኦሮሚያ የሚደረጉ የሕዝብ አመጾች የኢትዮጵያን ሰንደቅ አላማ ሳይሆን የኦነግን ባንዲራ በመያዝ የሚደረጉ ናቸው:: የኦነግ ሰዎች ሲያወሩ ኢትዮጵያን እና ኦሮሚያን ለያይተው ነው:: ሌሎቻችንም ብንሆን ይህን አባባል የለመድነው ይመስላል:: ኢትዮጵያውያን እና ኦሮሞወች በየተቃውሞ መድረኩ የየራሳቸውን ባንዲራ ይዘው ጐን ለጐን ሲሰለፉ እያየን ነው:: ኦነግ የኦሮሚያን ካርታ ካወጣ ብዙ አመታትን አስቆጥሯል:: የኦሮሚያን የሽግግር መንግስት ሰነድ ለማርቀቅ እና የመከላከያ ሰራዊት ለመገንባት እንደታቀደም እየሰማን ነው:: የቀረው የወያኔን ውድቀት ተከትሎ የኦሮሚያን ነጻነት ማወጅ ብቻ ነው::

 

“ብቻ ወያኔ ይውደቅ” የሚሉ ኢትዮጵያዊያኖች የኦነግን አደገኛና አፍራሽ አካሄድ እየተገነዘቡ አይመስልም::  ይህ የተዛባ አመለካከት በፍጥነት ሊታረም ይገባል:: መላው ሀገር ወዳድ ኢትዮጵያውያን የኦነጎችን እና የወያኔን አፍራሽ እንቅስቃሴ በእኩል በንቃት በመከታተል የሚሸርቡትን ሴራ ማክሸፍ ይኖርበታል:: የኦነግ ያፈጠጠ ፍላጎት ኦሮሚያን ከኢትዮጵያ መገንጠል ነው:: ይህ የመገንጠል መዘዝ በኢትዮጵያ እና በኤርትራ መሀል ከፈጠረው ውድመት ሽህ ጊዜ ለሚበልጥ ጉዳት የሚዳርግ: ክልሉን የጦር ቀጣና ለማድረግ በሚያስቡ ታሪካዊ ጠላቶቻችን የተሰላ ተንኮል ነው:: ከኢትዮጵያ የመቶ አመት የቤት ስራ ውስጥ አንዱ የሆነው የኦነግ እንቅስቃሴ ካልተነቃበት ሊታረም የማይችል ጥፋት የሚያስከትል ይሆናል::

 

አንዳንድ የአማራ አክቲቭስቶች የኦነግን የነጻ ሀገር ምስረታ ፍላጎት እንደአደጋ አለማየታቸው ገርሞኛል:: ለመሆኑ ኦነግ ነጻ ኦሮሚያን እንደሀገር መመስረት ቢፈልግ የቱን ይዞ የቱን ትቶ ነው? አማራው ራሴን ችየ ሀገር እመሰርታለሁ ቢልስ የትኛውን የሀገሪቱ አካባቢ ይዞ ነው:: “ብቻ ወያኔ ይውደቅ!” የሚለው አባባል ፍጹም የተሳሳተ ነው:: ኦነግ የራሱ ካርታ እንዳለው ከዚህ በፊት ባወጣቸው ሰነዶች ላይ አይተናል:: ኦሮሞወች ነጻ ሀገር ለመመስረት ከፈለጉ ይህን ፍላጎታቸውን ማንም ሊያዳፍነው አይችልም ብለው የሚሉት ሰዎች ምን እያሰቡ ነው? በዚህ ሰነድ ላይ ተስማምተዋል ማለት ነው? ወይስ የኦነግን ጉዳይ በይደር ትተን ወያኔን ከስጣልን ካስወገድን በኋላ እንመለስበታለን ተብሎ ታስቦ ነው?

 

ከኦነግ ጀርባ የተሰለፈ ጠንካራ ኃይል መኖሩ መዘንጋት የለበትም:: አሁን እየተደመጠ ያለው የግብጽ መንግሥት ለኦነግ ማንኛውንም ድጋፍ ለማድረግ ቃል እንደገባ ነው:: ግብጽ የኢትዮጵያን መዳከም እና መከፋፈል አጥብቃ የምትፈልግ መቸም ቢሆን የማትተኛልን ታሪካዊ ጠላታችን ናት:: ኦነግ ስለወደፊቱ መጨነቅ የሚፈልግ ድርጅት አይደለም:: ወያኔ በበኩሉ ለብዙ ሽህ አመታት ኢትዮጵያን በደምና በአጥንቱ አስከብሮ ያቆየውን የአንድነት ኃይሉን አከርካሪ መስበሩን በኩራት ነግሮናል:: በዚህ የዱርየ ስራቸው የሚኩራሩት የወያኔ አመራሮች የአንድነት ተሟጋቾችን አዳክመው ሀገራችንን ለጥቃት ማጋለጣቸውን የሚያስተውሉበት ዐዕምሮ ያልታደሉ መሆናቸውን አስመስክረዋል:: ወያኔ ብሔር-ብሔረሰቦችን ለማፈን ከላይ ያስቀመጣቸውን የድርጅት አመራሮች እና ሰራዊቱን ተማምኖ ሕዝብን ንቋል:: በበብሔር-ብሔረሰቦች  መሀል መተሳሰብ እንዳይኖር አድርጎ በመሀከላቸው የጥላቻ ዘር ሲዘራ ኖሯል:: ከአማራ ክልል እና ከአፋር ክልል ቆርሶ በጉልበት ወደትግራይ በማካለሉ ከአጐራባች ክልሎች ጋር ጠብ ፈጥሯል:: ኢትዮጵያ ብትፈራርስ ወያኔም ሆነ የትግራይ ሕዝብ  እንዴት ሊጠቀሙ እንደሚችሉ አይታወቅም:: “ብልህ የአመቱን ሞኝ የእለቱን” የሚለው አባባል ጊዜው አልፎበት በአዲሱ ፋሽን ሁሉም የእለቱን ናፋቂ ሆኗል:: ነገ ምን ይዞ ይመጣ ይሆን እያሉ የሚጨነቁ ሰዎች ግን አልጠፉም:: አንዳንዴ ለምኑም ግድ የሌላቸው ሰዎች ያስቀናሉ:: ዞሮ ዞሮ በኢትዮጵያ ላይ እየደረሰ ላለውና ወደፊት ለሚመጣው ችግር በዋናነት ተጠያቂው ትግራይ-ወለዱ ወያኔ ነው::

 

የሰው ልጅ ትልቁ ጥንካሬ ተስፋ ነው:: እና አሁንም ከችግር የመውጫ መንገዶች ጨርሰው አልተዘጉም ብለን ተስፋ እናድርግ:: የአንዳንድ ሀገር ወዳድ ወገኖች የመንፈስ ጥንካሬ የሁላችንም ተስፋ ነው::  ስለሀገር እና ስለሕዝብ አብዝተው የሚጨነቁ ሰዎች ደከመን ሰለቸን ሳይሉ መፍትሄ ለማምጣት የሚያደርጉት ጥረት ተጠናክሮ መቀጠል አለበት:: ያለፈውን እና አሁን ያለውን ሁኔታ ገምግሞ የወደፊቱን ለመተንበይ  ለአንዳንዶቻችን ከባድ ሊሆን ይችላል:: እኔ እራሴ ደርግ ከወደቀ በኋላ እንኳ የደርግን ውድቀት አምኘ መቀበል አቅቶኝ ከዛሬ ነገ ተመልሶ ይመጣል እያልሁ ሳስብ ነበር:: የወቅቱን ሁኔታ በጥሞና መገምገም ለቻለ ኢትዮጵያን የገጠማት ፈተና እጅግ ከባድ መሆኑን ይረዳል:: አይመጣም ያልነው የሚመጣበት አይሆንም ያልነው የሚሆንበት ብዙ አጋጣሚ አለ:: ፈረንጆች Expect the worst የሚሉት ለቀልድ ሳይሆን መጥፎ አጋጣሚ ከመጥፎ ሁኔታ ብቻ ሳይሆን ከመልካም ሁኔታ መሀልም ሊከሰት እንደሚችል ግንዛቤ ተይዞ ጥንቃቄ ማድረግ እንደሚገባ ሲመክሩ ነው:: ስለዚህ እያንዳንዷን ርምጃ በጥንቃቄ ካልተራመድናት በሆይ ሆይታ የሚደረግ ጉዞ ከድጡ ወደማጡ ሊከተን ይችላል:: የሚያሳስበን የአሁኑ ችግር ብቻ ሳይሆን የወደፊት ኑሯችንም ጭምር ነው::

 

ትንሳኤ ለኢትዮጵያ!


ወታደሮች በካምፕ ውስጥ ያላቸው እንቅስቃሴ እንዲገደብና ፈቃድ እንዳይሰጣቸው ተደረገ።

0
0

በርካታ ወታደሮች በቡድን መጥፋት አንዲሁም በካምፕ ውስጥ የተደረጉ የተኩስ ልውውጦችን ተከትሎ በምስራቅ እዝ የሚገኘው የሕወሓት መኮንኖች ቡድ በሰጠው መመሪያ መሰረት ወታደሮች በካምፕ ውስጥ ያላቸው እንቅስቃሴ እንዲገደብና ፈቃድ እንዳይሰጣቸው ተደረገ። ቦምብ መታጠቅና ስብሰባ ላልተወሰነ ጊዜ ቆሟል። ሲሉ የእዙ ወታደራዊ ደህንነት ኣባል የሆኑ ኣንድ ሰው የላከት መረጃ ይጠቁማል። ወታደራዊ ደህንነቱ እንዳሉት የሶማሊያና የትግራይ ተወላጅ የሆኑ ወታደሮች ተለይተው ጠንካራ የሆነ የጥላቻና የክፍት ምክሮች እንደሚሰጣቸው በዙሪያቸው ያሉትን ሌሎች ወታደሮች እንዳያምኑና እንዲሰልሉ እየተደረገ መሆኑ ታውቋል።

photo file

photo file


በየወታደራዊ ካምፖች በመላው ሃገሪቱ ከዚህ ቀደም ታይቶ በማይታወቅ መልኩ ከፍተኛ የሆነ የስለላ ስራ እንደሚሰራ የሚናገሩት ምንጮች ኣብዛኛው ወታደሮች ዝምታን ቢመርጡም ለስርዓቱ ያላቸውን ተቃውሞ ድንገት ያፈነዱታል ተብሎ ተፈርቷል።ለወታደሮች የሚሰጣቸው ጥይት ኣነስተኛ ሲሆን ቦምብን የመሳሰሉ የፍንዳታ መሳሪያዎች እንዳይታጠቁ ተከልክለዋል። ቦምብ መታጠቅና እንደላውንቸር ያሉ መሳሪያዎችን እንደ ዙ23 እና ታንክ መሰሎችን እንዲይዙ እንደቆጣጠሩ የሚደረጉት የትግራይ ተወላጆች ናቸው ሲሉ ምንጮቹ ለምንሊክ ሳልሳዊ ተናግረዋል።
ወታደሮቹ ፈቃድ እንዳያገኙና ስብሰባ እንዳይደረግ ያገዱት ወታደራዊ ኣዛዦች ምክንያታቸው ዛሬም ኣልሸባብ ገፍቶ ሃገራችንን እንዳይወራትና የሻእቢያ መጫወቻ እንዳንሆን የደርግ ወታደሮችን ታሪክ ኣስታውሱ በሚል ፕሮፓጋንዳ በማጀም ወታደሩ በተጤንቀቅ እንዲቆምና ስብሰባና ፈቃዳ በኣልስሀባብ በኩል ያለውን ችግር ሶማሊያ የዘመተው ጦራችን ካረጋጋው በኋላ ይደርሳል በማለት ፕሮፓጋንዳቸውን እየረጩ ይገኛሉ፥ከዚሁ ጋር በተያያዘ ዜና ሕወሓት የተመረዙ ምግቦችንና መጠጦች በተለያዩ መስመሮች ለመጠቀም ዝግጅት እያደረገ መሆኑን ወታደራዊ ደህንነቶች ጨምረው ኣስረድተዋል

Source:-Mereja.com

በዳያስፖራ ከትግራይ ተወላጆች የተሰጠ (3ኛ) መግለጫ

0
0

ህውሓት/ኢህአዴግ ቢሾፍቱ ላይ ባደረሰው አሰቃቂ እልቂት በጣም አዝነናል
የሽግግር መንግስት በአፋጣኝ ይቋቋም!

በዳያስፖራ ከትግራይ ተወላጆች የተሰጠ (3ኛ) መግለጫ

ባሳለፈነው እሁድ (22.01.2009) ከተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች የተሰባሰቡ ዜጎች በተገኙበት በቢሾፍቱ ከተማ በደማቅ ሁኔታ በመከበር ላይ በነበረው የኢሬቻ በዓል ላይ፣ ዜጎች በአፋኙ “መንግስት” ላይ ያላቸውን ተቃውሞ ባዶ እጃቸውን አጣምረው በሰላማዊ መንገድ በማሰማታቸው ምክንያት፣ ሰብአዊነት በጎደለውና ጭካኔ በተሞላበት የህውሓት/ኢህአዴግ አሰቃቂ እርምጃ የብዙኃን ህይወት ተቀጥፏል። የኦሮሞ ፌዴራሊስት ኮንግረስ ም/ሊቀመንበር አቶ ሙላቱ ገመቹ በቪኦኤ ቀርበው እንደገለፁት፣ የህውሓት/ኢህአዴግ ታጣቂዎች በፈፀሙት በዚህ አረመኔያዊ ጭፍጨፋ ምክንያት 678 ዜጎች መሞታቸው ተረጋግጧል። ከ400 በላይ ሰዎች በሞትና በህይወት መካከል ይገኙ የነበረ ሲሆን ትክክለኛ የሟቾች ቁጥር ከዚህ በላይም ሊያሻቅብ እንደሚችል ይገመታል።
እኛ ስማችን ከታች የተዘረዘረው የትግራይ ተወላጅ ኢትዮጵያውያን፣ ጭካኔ በተሞላበት በዚህ አረመኔያዊ ድርጊት በከፍተኛ ሁኔታ ማዘናችንን ለመግለፅ እንወዳለን። የተሰማንን ጥልቅ ሀዘን ለመግለፅ ቃላት ያጥሩናል። ህውሓት/ኢህአዴግ የፖለቲካና የኢኮኖሚ የበላይነቱን ለማስጠበቅ ሲል በዜጎች ላይ ያለውን አያያዝ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየከፋ በመሄድ፣ ዛሬ ህዝብን የሚያስተዳድር መንግስት ሳይሆን ህዝብን የሚያሸብር ወንበዴ መሆኑን በተግባር ያስመሰከረበት ዘግናኝ እልቂት ለማየት በቅተናል። በተለይ ደግሞ ይህን የሚያደርገው ህውሓት፣ የተለያዩ የብሔር ትንኮሳዎችን እያራገበና ከመቼውም በላይ በትግራይ ህዝብ ስም እየነገደና ጥላቻን እየበተነ ባለበት በዚህ ወቅት በመሆኑ ሀዘናችንን የከበደ አድርጎታል።
ቀደም ሲል ባወጣነው የጋራ መግለጫ እንደጠቀስነው፣ ህውሓት/ኢህአዴግ ከስልጣኑ ወርዶ የሽግግር መንግስት ባገሪቱ ካልተመሰረተ፣ ስልጣን ላይ በሚቆይበት እያንዳንዱ ተጨማሪ ቀን በዜጎች ላይ የባሰ እልቂትን እያስከተለና የአገሪቱን ህልውና ይበልጥ አደጋ ላይ እየጣለ መዝለቁ አይቀሬ ነው። ህውሓት/ኢህአዴግ ከህዝብ ራሱን ነጥሎ በትምክህትና በጉልበት ረግጦ ለመግዛት የሚሞክረው አካሄድ መቼም ቢሆን ሊሳካለት እንደማይችል ተረድቶ የሽግግር መንግስት ለማቋቋም ቢሰራ ለሁሉም የሚበጅ ነውና በድጋሚ ለመምከርና ለመዘከር እንወዳለን።
ህውሓት/ኢህአዴግና የኢትዮጵያ ህዝብ የገቡበት ቅራኔ ከዚህ ብኋላ በሌላ በማንኛውም መንገድ ሊታረቅ የሚችል ቅራኔ ባለመሆኑ መፍትሔው የሽግግር መንግስት በመመስረት ህዝብ በነፃና ገለልተኛ ምርጫ ይሆነኛል የሚለውን ስርዓት እንዲመርጥ መንገድ ማመቻቸት ብቻና ብቻ ነው የሚለው እምነታችን አሁንም ፅኑ ነው።
ይህ እንዳለ ሆነ፣ ካለፈው ባህሪው ተነስተን ህውሓት/ኢህአዴግ በጎ ፈቃደኝነት ይኖረዋል ብለን ለማመን ስለምንቸገር፣ ይህን የማሳከት ሃላፊነቱና የዜግነት ግዴታው የተጣለው በመላው አገር ወዳድ ኢትዮጵያዊ ላይ መሆኑን በፅኑ እናምናለን። በመሆኑም በመላ አገሪቱ ለነፃነቱ በጋራ እየተነሳ እንዳለው ህዝባችን፣ በተለያዩ የተቃውሚ ጎራ፣ የሲቪክ ተቋማት፣ የእምነት ተቋማት፣ እና የሙያ ማህበራት ስር የምንገኝ ኢትዮጵያውያን (በተለይም በመሪነት ደረጃ የተቀመጥን ዜጎች) ጊዜያዊ ልዩነታችንን ወደጎን ብለንና የጋራ መድረክ በማዘጋጀት ሁሉንም ያቀፈና ያሳተፈ የሽግግር መንግስት የመፍጠር ሂደት ከወዲሁ እንድንጀምር በዚህ አጋጣሚ ጥሪያችንን ለማስተላለፍ እንወዳለን።
ከዚህ በተጓዳኝ ግልፅ ለማድረግ የምንፈልገው አንድ ነገር አለ። ይኸውም ህውሓት በትግራይ ህዝብ ስም የሚነግደውና በትግራይ ህዝብ ስም ጥላቻ የሚነዛው አልበቃ ብሎት፣ በተለያዩ የአገሪቱ ክፍል የሚገኙ የትግራይ ተወላጆችን በማታለል ከቤት ንበረታቸው እያፈነቀለ ወደ ትግራይ ለማጓጓዝ እንቅስቃሴ መጀመሩን ከታማኝ ምንጮች ለመረዳት ችለናል። ይህንን ሴራውን ለማሳካት በትግራይ ተወላጆች ላይ ሃላፊነት የጎደለው እርምጃ ሊወስድ እንደሚችል ሁሉ ጥቆማዎች ደርሰውናል። ይህን የአቋም መግለጫ በምናዘጋጅበት ሰዓት አንዳንድ የትግራይ ተወላጆች ከኦሮሚያ ክልል መውጣት መጀመራቸውን አረጋግጠናል።
የትግራይ ተወላጅ ኢትዮጵያውያን በህውሓት ፕሮፓጋንዳና ሽንገላ ተታለው ለዓመታት ጎጆ ቀልሰው ከኖሩበትና ጥረው ግረው ካፈሩት ቤት ንብረታቸው ተፈናቅለው፣ ከኢትዮጵያውያን ወገኖቻቸው በመነጠል አፋኙና ነፍሰ በላው የህውሓት ቡድን ባዘጋጀላቸው ወጥመድ እንዳይገቡ ለማስጠንቀቅ እንወዳለን። ዛሬ ለትግራይ ህዝብ ከህውሓት በላይ ሌላ ጠላት እንደሌለው እያንዳንዱ የትግራይ ተወላጅ ሊያውቀው ይገባል። በህውሓት ስር ያሉ ወሮበላዎች ለትግራይ ህዝብ ቀርቶ አብረው ለታገሉ ጓዶቻቸውና ለቤተሰቦቻቸውም ምህረት የማያውቁ አረመኔዎች መሆናቸውን ሁሉም ኢትዮጵያዊ ሊገነዘብ ይገባል።
በሁሉም የአገሪቱ ክፍል የምትኖሩ የትግራይ ተወላጅ ወገኖቻችን ህውሓት ባዘጋጀላችሁ ወጥመድ ሳትገቡና የህውሓትን ህልም አሳክታችሁ ራሳችሁን መቋጫ ለሌለው ሰቆቃ ሳትዳርጉ በፊት፣ በያላችሁበት ከሌላው ኢትዮጵያዊ ወገናችሁ ጋር በጋራ በመቆም ለነፃነታችሁ እንድትታገሉ በዚህ አጋጣሚ ጥሪያችንን እናቀርባለን። ሁሉም ነፃ ካልወጣ ማንም ነፃ ሊወጣ እንደማይችል ተገንዝበን ከሌሎች ኢትዮጵያውያን ወገኖቻችን ጎን በጋራ በመቆም ለነፃነት የሚደረገውን ትግል በያለንበት እንድንቀላቀል በድጋሚ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን።
በአገሪቱ በሁሉም አቅጣጫ የምትኖሩ ኢትዮጵያውያን ወገኖቻችን፣ ለዘመናት በመካከላችሁ አብረዋችሁ የኖሩ የትግራይ ተወላጅ ወገኖቻችሁ ከማንኛውም ኃይል ሊደርስባቸው ከሚችል ጥቃት የመጠበቅ አደራ ተጥሎባችኋል። አብዛኛው የትግራይ ተወላጅ ዜጋ እንደማንኛውም ኢትዮጵያዊ ወገኑ በአፈናና በጭቆና ስር የሚኖር ወንድማችሁ በመሆኑ፣ በተለይ ህውሓት ህልሙን ለማሳካት ሊፈፅምባቸው ከሚችል ደባ ለመጠበቅና ለነፃነት ትግሉ ከጎናችሁ ለማሰለፍ የዜግነት ግዴታችሁን እንደትወጡ እንማፀናለን።
በማጠቃለል በቢሾፍቱ በደረሰ አሰቃቂ እልቂት ልባችን የደማ መሆኑን በድጋሚ እየገለፅን፣ ለቤተሰቦቻቸው፣ ለወዳጅ ዘመዶቻቸውና በአጠቃላይ ሀዘን ላይ ለተቀመጠው ኢትዮጵያዊ ወገናቸው እግዚአብሔር መፅናናቱን እንዲሰጥልን፣ የሙታንን ነፍስ በሰላም እንዲያሳርፍልን እንመኛለን። እግዚአብሔር በምህረቱ ይጎብኘን፤ አገራችንንም ይባርክልን። አሜን!
የስም ዝርዝር
1. ህይወት ተሰማ
2. ሓረገወይኒ:ገ/ኢየሱስ
3. ሕሉፍ በርሀ
4. ሜሮን አብርሃ
5. ሲራክ ኣማረ
6. ስልጣን ኣለነ
7. በላቸው ለማ
8. በየነ ገብራይ
9. ብሩክ እንግዳ
10. ተስፋዬ መሓሪ
11. ተስፋይ ኣፅብሃ
12. ታደሰ በርሀ
13. ታደሰ ገብረእዝጊ
14. ነጋሲ በየነ
15. ናትናኤል ኣስመላሽ
16. አሰር አሉላ
17. አባይ ኪሮስ
18. ዶክተር ኣረጋዊ በርሀ
19. ኣብራሃ በላይ
20. ኣብርሃም ኀይለ
21. ኤልያስ በየነ
22. ኪዳነ ኃይሌ
23. ኪዳነማርያም ፀጋይ
24. ካሕሳይ በርሀ
25. ዘልኣለም ንርአ
26. ዮሃንስ በርሀ
27. ዮሴፍ ብርሃነ
28. ዮናስ ሓጎስ
29. ዮናስ መብራህቱ
30. ደስታ ኣየነው
31. ገብረኪዳን ዳዊት
32. ዶክተር ግደይ ኣሰፋ
33. ጥላሁን አረፈ
34. የማነ ምትኩ
35. ሸዋዬ ሽፈራው
36. ደረጀ ገ/ሂወት
ማሳሰቢያ!
ከኢትዮጵያ ውስጥ ሆነው መረጃ በማቀበልና አንዳንድ እንቅስቃሴዎችን በማስተባበር እየተባበሩን ያሉ የትግራይ ተወላጆች ቁጥር እየጨመረ ሲሆን፣ በርካቶች ስማቸው እዚህ እንዲካተት የፈቀዱ ቢሆንም ሊደርስባቸው ከሚችል አደጋ ለመጠንቀቅ ስንል በሚስጥር ለመጠበቅ ተገደናል።
አስተባባሪዎቹ
ህውሓት/ኢህአዴግ አብ ቢሾፍቱ ብዘብፅሖ ህልቂት ብጣዕሚ
ጊዜያዊ ናይ ሽግግር መንግስት ብቅልጡፍ ክጣየሽ አለዎ!
ተጋሩ አሕዋትና ህውሓት አብ ዘዳለዎ መፃወዲያ ከይንአቱ ንጠንቀቕ
ካብ ተወለድቲ ትግራይ ዝተፈነወ 3ይ መግለፂ
መስከረም 27 2009
አብ ዝሓለፈ ሰንበት (መስከረም 22 2009) ካብ ዝተፈላለዩ ክፍሊታት ሀገርና ዝተአኻኸቡ ዜጋታት አብ ቢሾፍቱ ከተማ ብድምቀት የኽብሩ አብ ዝነበሩሉ በዓል ኢሬቻ፣ ኢትዮጵያውያን ንአምባገነን “መንግስቲ” ኢትዮጵያ ዘለዎም ተቓውሞ ብሰላማዊ መንገዲ ኢዶም አጣሚሮም ብምግላፆም ምኽንያት፣ ሰብአዊነት ብዝጎዶሎን ጭካነ ብዝተሞለኦን ናይ ህውሓት/ኢህአዴግ ስጉምቲ ብዙሓት ኢትዮጵያውያን መተካእታ ዘይብላ ሓንቲ ህይወቶም ስኢኖም እዮም። ም/ሊቀመንበር ኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ ፓርቲ አይተ ሙላቱ ገመቹ ንቪኦኤ-አምሓርኛ ቀሪቦም ዝሀብዎ መረዳእታ ከምዝሕብሮ፣ ወታደራት ህውሓት/ኢህአዴግ ብዝፈፀምዎ አረመኔያዊ ጭፍጨፋ ምኽንያት 678 ሰባት ከምዝሞቱ ተረጋጊፁ እዩ። ልዕሊ 400 ሰባት ድማ አብ መንጎ ሞትን ሀለዋትን ከምዝርከቡ ዝገለፁ እንትኾን፣ ትኽክለኛ ቑፅሪ ዝሞቱ ሰባት ክውስኽ ከምዝኽእል ይግመት።
ንሕና ሽምና አብ ታሕቲ ዝተጠቐሰ ተወለድቲ ትግራይ ኢትዮጵያውያን፣ በዚ ጭካነ ዝተመልኦ አረመኔያዊ ስጉምቲ ህውሓት/ኢህአዴግ አዚና ዝሓዘንና ምዃንና ክንገልፅ ንፈቱ። ዝተሰመዐና መሪር ሓዘን ንምግላፅ ቃላት ይሓፁርና እዮም። ህውሓት/ኢህአዴግ ምእንታን ፖለቲካዊን ኢኮኖሚያዊን ዕብለላኡ ክሕልው ክብል አብ ዜጋታት ዘለዎ አተሓሕዛ ካብ ጊዜ ናብ ጊዜ እናከፈአ ክኸይድ ብምግባር፣ ሎሚ ህዝቢ ዘመሓድር መንግስት ከይኾነስ ንህዝቢ ዘሸብር ሽፍታ ከምዝኾኒ ብተግባር ዘመስከረሉ ህልቂት ንምርአይ በቒዕና አለና። ብፍላይ ድማ ንዚ ዝገብር ዘሎ ህውሓት፣ ዝተፈላለዩ ብሔር መሰረት ዝገበሩ ቅርሕንቲ አብ መንጎ ህዝቢታት ኢትዮጵያ እናፈጠረን ብሽም ተጋሩ እንዳነገደን አብ ዘርከበሉ አብዚ ሕዚ እዋን ምዃኑ ሓዘንና ዝኸበደ ገይርዎ አሎ።
ቅድም ክብል ብአምሓርኛ አብዝፈነናዬ ናይ ሓባር መግለፂ ከምዝጠቐስናዮ፣ ህውሓት/ኢህአዴግ ካብ ስልጣኑ ወሪዱ ጊዜያዊ ናይ ሽግግር መንግስቲ ክጣየሽ እንተዘይገይሩ፣ አብ ስልጣን አብ ዝፀንሐሉ ሕድ ሕድ ዕለት ካብ ዝሓለፈ ዝገደደ ህልቂት አብ ህዝቢ እንዳብፅሐን ህልውና እታ ሀገር ናብ ዝኸፈአ ሓደጋ እንዳእተወን ከምዝኸይድ ዘጠራጥር አይኮነን። ህውሓት/ኢህአዴግ ካብ ህዝቢ ንዓርሱ ነፂሉ፣ ብትምክሕቲን በጉልበትን ረጊፁ ንምግዛእ ዝፍትኖ ዘሎ አካይዳ አብ ዝኾነ ይኹን እዋን ክሰምረሉ ከምዘይኽእል ተረዲኡ ጊዜያዊ ናይ ሽግግር መንግስቲ ንኸጣይሽ ደጊምና ንላቦ።
ህውሓት/ኢህአዴግ ምስ ህዝቢ ኢትዮጵያ አቲዎ ዘሎ ቅርሕንቲ ድሕሪ ሕዚ ብኻሊእ ብማንኛውም መንገዲ ክሽምገል ዘይኽእል ብምኻኑ፣ ብሕታዊ መፍትሒ እቲ አቲዎ ዘሎ ቅልውላው ጊዜያዊ ናይ ሽግግር መንግስቲ ብምጥያሽ ህዝቢ ኢትዮጵያ ብነፃ ምርጫ ዝመሰሎ ስርዓት ንኽተክል ኹነታት ምምችቻው ጥራሕ እዩ ዝብል እምነትና ፅኑዕ እዩ።
እዚ ኸምዘሎ ኾይኑ፣ ካብ ሕሉፍ ባህሪያት ህውሓት/ኢህአዴግ ተበጊስና ንዚ ንምፍፃም ድልውነትን ውፉይነትን ይህልዎ እዩ ኢልና ንምእማን ስለ እንፅገም፣ ንዚ ናይ ምፍፃም ሓላፊነት አብ ኹሉ ፈተዊ ሀገርን ተገዳሲን ወገን ዝተደብረየ ሓላፍነት ምዃኑ ንአምን። ስለዝኾነ ድማ አሰር እቲ አብ መላእ ሀገር ንናፅነቱ ዝቃለስ ዘሎ ህዝብና ተኸቲልና፣ አብ ዝተፈላለዩ ናይ ተቓዋሚ ፓርቲታት፣ ሲቪክ ማሕበራትን ናይ እምነት ትካላትን ብአባልነት ንርከብ ዜጋታት (ብፍላይ ድማ አብ አመራርሓ ዘለና አካላት) ጊዜያዊ አፈላላይና ንጎኒ ብምባል ተቐራሪብና ናይ ሓባር መድረኽ ብምድላው፣ ንኹሉ ዘሳተፈን ዝሓቖፈን ናይ ሽግግር መንግስቲ ንምፍጣር ምንቅስቓስ ንኽንገብር ፃዊዕትና ነቕርብ።
ምስ እዚ ተተሓዙ ብፍላይ ንተጋሩ አሕዋትና መተሓሳሰቢ ክንህብ ንፈቱ። ህውሓት/ኢህአዴግ ብተጋሩ ሽም ዝንግዶን ዘሰራጭዎ ዘሎ ፅልኢታትን ከይአኸሎ፣ አብ ዝተፈላልዩ ክፍሊታት ሀገርና ንዝርከቡ ተጋሩ አሕዋትና አታሊሉ ካብ ገዝኦምን ንብረቶምን በምፍንቓል ናብ ትግራይ ከጓዓዕዝ ምንቅስቓስ ከምዝጀመረ ካብ እሙናት ሰባት ሓበሬታ ረኺብና አለና። እዚ መግለፂ አብ ነዳልወሉ እዋን ሓደ ሓደ ተጋሩ አሕዋትና ካብ ዝተፈላለዩ ኸባቢታት ኦሮሚያ ምውፃእ ከምዝጀመሩ አረጋጊፅና አለና።
ተጋሩ አሕዋትና ብናይ ህውሓት ፕሮፓጋንዳን ተንኮል ተዓሺኹም ንዓመታት ጎጆ አጣይሽኹም ካብ ትነብሩሉን ብርሃፅኩም ፅዒርኩም ካብ ዘጥረኽምዎን ንብረትኹምን ተፈናቒልኹም፣ ካብ ኢትዮጵያዊ ወገንኹም ብምንፃል ህውሓት ናብ ዘዳለወልኩም መፃወዲያ ከይትአትዉ አጥቢቕና ክነጠንቅቐኩም ንፈቱ። ሎሚ ንህዝቢ ትግራይ ከብ ህውሓት ንላዕሊ ፀላኢ ከምዘይብሉ ተረዲእኹም ንማዕርነትን ናፅነትን አብ ዝግበር ዘሎ ቓልሲ ምስቲ ኻሊእ ኢትዮጵያዊ ወገንኹም ብምትሕብባር በብዘለኽምዎ ክትቃለሱ ፃዊዕትና ነቕርብ። ህውሓት ንህዝቢ ትግራይ ይትረፍ፣ ንመቓልስቶምን ንቤተሰቦምን ምሕረት ዘይፈልጡ አረመኔታትን ፈተውቲ ኸርሶምን ዝኾኑ ገበነኛታት ዝተሰግሰጉሉ ናይ ሸፋቱ ድርጅት ምኻኑ ተረዲእና ከይተገራህና ዓጢቕና ክንቃለሶም ኸምዘለና ክነተሓሳስብ ንፈቱ። እዚ እንድሕር ደአ ዘይኾይኑ፣ ህውሓት አ ብዘዳለዉልና መፃወዲያ አቲና ንመሪር ጭቆና መግዛእቲን ዓርስና አሕሊፍና ንምሀብ ከምዝፈቐድናን ብፍላይ ድማ መሕብኢ ገበናቶም ንምዃን ክምዝተስማዕማዕናን ክንፈልጦ ይግባእ።
አብ መላእ ሀገርና ዝርከቡ ካልኦት ወገናትና እውን ንዓመታት ሀገርና ኢሎም አብ መንጎኹም ንዝነብሩ ዘለዉ ተጋሩ ወገናትኹም ካብ ዝኾነ ይኹን ሓይሊ ክበፅሖም ካብ ዝኽእል መጥቃዕቲ ናይ ምሕላው ሓደራ ተዋሂብኩም አሎ። መብዛሕትኡ ትግራዋይ ከምቲ ኻሊእ ኢትዮጵያዊ ወገኑን ብዓፈና፣ ጭቆናን ድኽነትን ዝነብር ሓውኹም ስለዝኾነ፣ ብፍላይ ድማ ህውሓት ንቲ እከይ ሕልሙ ንምሳኽዕ ክብል ክወስደሎም ካብ ዝኽእል አረመኔያዊ ስጉምቲ ናይ ምሕላው ሕድሪ ተዋሂብኩም አሎ። አብ ጎንኹም አሰሊፍኩም ንናፅነቶም ብሓባር ንኽተቃልሱን ናይ ዜግነት ግዴታኹም ንክትዋፅኡን ንሓትት። ኹልና ነፃ ተዘይወፂና ማንም ነፃ ክወፅእ ስለዘይኽእል፣ ብሓባር ምቅላስ አገዳሲ ከምዝኾነ ክነስምረሉ ንፈቱ።
በምጥቕላል አብ ቢሾፍቱ ብዝበፅሐ ዘስካሕክሕ ህልቂት ልብና ኸምዝደመየ ዳግም እንዳገለፅና፣ አብ ሓዘን ንዝተቐመጡ ቤተሰቦም፣ ወለዶም፣ አዝማዶምን መሓዙቶምን ከምኡ’ውን አብ ሓዘን ንዝርኸቡ ኹሎም ኢትዮጵያዊ ወገናትና እግዚአብሄር ፅንዓት ንኽህቦምን ንምነ። ንቶም ብግፍዒ ዝሞቱ ወገናትና ‘ውን መንግስተ ሰማያት የዋርሰልና። አምላኽ ብምሕረቱ ይጎብነየና፣ ሀገርና ይባርኸልና። አሜን!
ሽም ዝርዝር
1. ህይወት ተሰማ
2. ሓረገወይኒ:ገ/ኢየሱስ
3. ሕሉፍ በርሀ
4. ሜሮን አብርሃ
5. ሲራክ ኣማረ
6. ስልጣን ኣለነ
7. በላቸው ለማ
8. በየነ ገብራይ
9. ብሩክ እንግዳ
10. ተስፋዬ መሓሪ
11. ተስፋይ ኣፅብሃ
12. ታደሰ በርሀ
13. ታደሰ ገብረእዝጊ
14. ነጋሲ በየነ
15. ናትናኤል ኣስመላሽ
16. አሰር አሉላ
17. አባይ ኪሮስ
18. ዶክተር ኣረጋዊ በርሀ
19. ኣብራሃ በላይ
20. ኣብርሃም ኀይለ
21. ኤልያስ በየነ
22. ኪዳነ ኃይሌ
23. ኪዳነማርያም ፀጋይ
24. ካሕሳይ በርሀ
25. ዘልኣለም ንርአ
26. ዮሃንስ በርሀ
27. ዮሴፍ ብርሃነ
28. ዮናስ ሓጎስ
29. ዮናስ መብራህቱ
30. ደስታ ኣየነው
31. ገብረኪዳን ዳዊት
32. ዶክተር ግደይ ኣሰፋ
33. ጥላሁን አረፈ
34. የማነ ምትኩ
35. ሸዋዬ ሽፈራው
36. ደረጀ ገ/ሂወት

የማለዳ ወግ …አባቱ ፖለቲከኛና እውቁ ባለሙያ ኢንጅነር ሃይሉ ሻወል!

0
0

* ኢንጅኔር ሃይሉ ሻዎል ህልማቸው የተሳካ ፖለቲከኛ አይባሉም
* ለዲሞክራሲ፣ መእኩልነትና ፍትህ መስፈን የቻሉትን ሁሉ አድርገዋል
* በኢትዮጵያ ትንሳኤ የትጉሁ አባቱ ፖለቲከኛ ድካም በክብር ይወሳል
* ዛሬ ህዝብ ፍትህ ነጻነትን በአደባባይ ጠይቋል፣ ይህም የሃይሉም ትጋት ውጤት ነው
ኢንጅነር ሃይሉ ሻዎልን በወጣትነት የጋዜጠኝነት ህይዎቴ ደጋግሞ የማግኘት እድል አጋጥሞኛል … ኢትዮጵያን በነፍስ ይወዷታል ፣ ግማሽ ክፍለ ዘመን ለሚጠጋ የጎልማሳ እድሜ አስተምራ ለወግ ማዕረግ አብቅታቸዋለችና ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይሉ አገልግለዋታል ! ሃይሉ ቁጡና ኃይለኛ ናቸው ቢባክም ካልነኳቸው አይነኩም … ላመኑነት ወደ ኋላ ማለት አያውቁም … በተለይ በሀገራቸውና በህዝባቸው ቀልድ የለም ! ደፋር ናቸው ፣ ያመኑበትን በግላጭ ከመናገር አያፈገፍጉም ምነዋ ግትር ፖለቲከኛ መሆንዎ ሲባሉ ” በሀገሬና በህዝቤ ለመጣብኝ ግትር ነኝ !” በማለት እንቅጯን ይነግሩዋችኋል !
hailu
ኢንጅኔር ሃይሉ ሻዎል ፖለቲከኛ ያደረጋቸው የሀገራቸው ነገር አሳስቧቸው የአቅማቸውን ለማድረግ ነበር ወደ ፖለቲካው የገቡት … ፖለቲካው ደግሞ የእኛ ሀገር ፖለቲካ ፣ መሪዎች ደግሞ ለሃገር የማይበጅ ራዕይ አራማጅ ናቸውና ከሃይሉ ሻዎል ጋር አይጣጣሙ ም … በፖለቲካው ምህዳር ሰፍቶ ባይሰፋም ኢንጅነር ሃይሉ ሻወል የፖለቲካ ምህዳሩ ሰፍቶ ዲሞክራሲ፣ እኩልነትና ፍትህ ሰፍኖ ለውጥ ይመጣ ዘንድ የቻሉትን ሁሉ አድርገዋል ፣ ፍርሃታችን ካስወገዱት ፖለቲከኞ አንዱም ናቸው … ኢንጅኔር ሃይሉ ሻዎል እንደ እኩዮቻቸው ምሁራን የሩቅ ተመልካች ሳይሆኑ ግንባራቸውን ለጦር ሰጥተው እድሜያቸውን እስኪገፋ ጥረው ግረዋል !
ኢንጅኔር ሃይሉ ሻዎል ህልማቸው የተሳካ ፖለቲከኛ አይባሉም ፣ በህልፈታቸው ዋዜማ እርሳቸው ይጮሁ ይታገሉለት የነበረው ኢትዮጵያዊ ፍትህ ነጻነትን በአደባባይ እየጠየቀ መገኘቱ የሃይሉም ትጋት ውጤት ነው ባይ ነኝ ፣ በህልፈታቸው ዋዜማ ህብረቷ የማይናጋ ኢትዮጵያን የማየት እድል ባያገኙም ከጫፍ እስከ ጫፍ መብቱን እየጠየቀ ያለው ሃገሬ ድምጽና ጸሎት ምህላው ከተሳካ እሰየው ነው ፣ ተከፋፍላ ማየት የማይፈልጓት ኢትዮጵያ ትንሳኤ ሲበሰር የትጉሁ አባቱ ፖለቲከኛ ልፋት ድካም በክብር ይወሳል !
በእስከዛሬው የህይዎት ጉዞ ኢንጅኔር ሃይሉ ሻዎልም ስለሚወዷት ኢትዮጵያ እንደ ቀሩት የሀገር ባለውለታዎች አቀበት ፣ ቁልቁለት ወጥተው ወርደው ፣ ለፍተው ደክመው ተለይተውናል ፣ ስለ ኢትዮጵያ ለከፈሉት መስዋዕትነት ክብር ለሚገባው ከብር በመስጠት ኢንጅኔር ሃይሉ ሻዎል ክበር ሰጥተን እናመሰግናቸዋለን :(
ነፍስ ይማር አባት አለም !
ነቢዩ ሲራክ
መስከረም 27 ቀን 2009 ዓም

አለባብሰው ቢያርሱ ባረም ይመለሱ (ይሄይስ አእምሮ)

0
0

ማለባበስ በጣም ጎጂ ነው፡፡ አሁን የምንገኝበት ማኅበራዊና ፖለቲካዊ አጣብቂኝ እንደእስከዛሬው ዓይነት የሽፍንፍንና የጥግንግን አካሄድን የሚያስተናግድ አይደለም – አምርሯል፡፡ አካፋን አካፋ ማለት የሚገባበት ትክክለኛ ጊዜ ላይ ደርሰናል፡፡ አንድን እውነት ሺህ ጊዜ ብንሸፋፍነው መገለጡ አይቀርም፡፡ ሲገለጥ ደግሞ የሚያስቀይም ስዕል ጎልቶ የሚታይበት አጋጣሚ እየበዛ ይመጣና ከመገናኘት ይልቅ መለያየት የማያመልጡት አሳዛኝ ክስተት ይሆናል፡፡

በሰሞኑ የእሬቻ በዓል የተከሰተውን ከወያኔ በቀር ሁላችንም እናውቃለን፤ ወያኔዎች ግን “ጥቂት ሰዎች (ኦሮሞዎች) በተፈጠረው መጨናነቅ ተረጋግጠው” እንደሞቱ እንጂ (በውጪዎቹ stampede ሲሉ ሰምተዋልና) በነሱው ታዛዥ “ኢትዮጵያውያን” አልሞ ተኳሽ ወያኔያዊ አልቃኢዳዎች በመትረየስና በጭስ ጋዝ እንደተረፈረፉ ሊያምኑ አይፈልጉም፡፡

ከዚህ የእሬቻ ዕልቂት ሌሎቻችን ምን እንማራለን?

59cbcc0b93dc457ea0f6f5000f4fef1d_18

ከዚህ ዕልቂት የምንማረው ነገር እጅግ ብዙ ነው፡፡ በመሠረቱ ይህ ዕልቂት በጎሣ ላይ ያነጣጠረ እንዳልሆነ ማመን እፈልጋለሁ፡፡ ኢትዮጵያውያን ለወያኔ ከፋፋይ ሥርዓት እጅ ሰጥተን ሁሉንም ነገር ወደዘር እንመነዝረዋለን እንጂ በአንዱ ሰው ውስጥ ብዙ ዘር በሚገኝበት እንደኢትዮጵያ ባለ ሀገር ውስጥ ሙከራው የለም ማለት ባይቻልም አንድን ዘር ለይቶ የማጥቃት ሙከራ እምብዝም አይሳካም፡፡ ምክንያቱም በሕዝብ የዘመናት ማኅበረሰብኣዊ ሽመና የተነሣ ማኅበረሰቡ አንዱን ሲሉት ሌላውን ነው – ኦሮሞ ሲሉት ትግሬ ነው፤ ትግሬ ሲሉት ደግሞ አማራ ነው፤ ጎንደሬ ሲሉት አርሲ ነው – ወለጋ ሲሉት ደግሞ ሲዳሞ ነው፡፡ ሁሉም ተቀያይጦ አንዱን ስትገድለው በውስጡ ሌላውም አብሮ ይሞታል፡፡ ከዐማራና ትግሬ ወላጆች የተገኙ ልጆችን ብትፈጅ ላንተ አንዱን ወይ ሌላውን የገደልክ ይመስልሃል እንጂ ሁለቱንም ነው ባንድ ጥይት የፈጀሃቸው፡፡ እንደፍቅሬ ቶሎሳ አንድ ቀደም ያለ መጣጥፍ ከሆነ ከ80 በመቶ በላይ የሚሆነው የኢትዮጵያ ሕዝብ በመዋሃዱ አንዱን ከሌላው ለመለየት የሚቻል አይደለም – ወያኔዎች ውኃና ዘይት ሊያደርጉን ቀን ከሌት ቢማስኑም ፈጣሪ በፀጋው ወተትና ውኃ አድርጎ አንዳችንን በአንዳችን ውስጥ እንደሰም አቅልጦ ውሁድ ሻማና ጧፍ አድርጎናል፤ ጊዜ ይፍጅ እንጂ ደግሞ ወያኔ ያዞረብንን ትብታብ በአንድነት በጣጥሰን አንዲት ታሪካዊት ሀገራችንን በጋሪዮሽ የብርሃን ፀዳላችን የምናደምቅበት የነፃነት ዘመን በቅርቡ መምጣቱ አይቀርም፡፡

ቋንቋ እንደሆነ በመልመድ ወይም በመማር እንጂ በባሕርያዊ የደም ትልልፍና በሀብት ውርስ የፍርድ ሂደት ስለማይገኝ ዐማርኛ የማይችል “ዐማራ” በኦሮሞ ውስጥ ብታገኝ ወይም ትግርኛ የማይችል “ትግሬ” በኦሮሞ ውስጥ ብታገኝ ይህ ክስተት ከፍ ሲል የሰው ልጅ ዝቅ ሲል ደግሞ የኢትዮጵያውያን ልዩ መገለጫ በመሆኑ የሚያስደንቅ አይደለም፡፡ ለዚህም ነው የወያኔ የዘር ቀመር ወንዝ የማያሻግር ወፍ ዘራሽ የታሪክ አራሙቻ መሆኑ የሚነገረውና ሀገር አጥፊነቱ ዘወትር የሚገለጸው፡፡ ሰሚ በመጥፋቱ ግን ሀገርና ሕዝብ ላይ በቀላሉ ሊቀለበስ የማይችል ጉዳት እየደረሰ ነው፡፡ ደጋግ ሰዎች እየጠፉ በክፉዎች ተከበናልና አንድዬ ይሁነን፡፡

ለማለት የፈለግሁት በዚህ የእሬቻ በዓል የሞቱት ሁሉም ኢትዮጵያውያን እንጂ አንዱ ዘር ማለትም ኦሮሞ ተመርጦ እንዳልሆነ ለማስታወስ ነው፤ ይህንንም ስል የማንንም ወንጀል ለመደበቅ ሣይሆን እውነቱን ለመግለጽ ብቻ ነው፡፡ ስለዚህ ወያኔ በዚህ ዕልቂት የፈረደብን በሁላችንም ላይ እንደሆነ መረዳት አለብን፡፡ ለነገሩ በዓሉን ለማክበር ከሁሉም ሥፍራዎችና ከሁሉም ጎሣዎች የተሰባሰቡ ኢትዮጵያውያን በሥፍራው በመገኘታቸው የኦሮሞ ሟች ቁጥር ሊበዛ እንደሚችል ቢገመትም ሁሉም ሞቷል ማለት እንችላለን፡፡ ማንም ይሙት ማን ግን የሞተው ሰው በመሆኑ፣ በዚያም ላይ ምናልባት ሁሉም ኢትዮጵያውያን መሆናቸው ስለሚገመት የሀዘኑን ምንጭ ወያኔን ሳይጨምር ሀዘኑ የሁላችንና የመላዋ ሀገራችን ነው፡፡ ነፍስ ይማር፡፡

ፍርዱ በሁላችንም ላይ ከሆነ ዘንዳ በወያኔ ላይ መነሳት ያለብን ሁላችንም በጋራ ሆነን ነው፡፡ የያዝነው መንገድ ግን እንደዚህ አይደለም ወይም አይመስለኝም፡፡ ጥቃቱ በሁላችንም ላይ የሚደርስ ሆኖ ሳለ የትግላችን አቅጣጫ ግን የተፈናጅራ (የተለያዬና ርስ በርስ የሚቃረን) ሆኖ ለኛ ተጨማሪ ዕልቂትን የሚያስከትል ለጠላቶቻችንና ለገዳዮቻችን ደግሞ ሠርግና ምላሽ ሆኖ ጮቤ የሚያስረግጣቸው ነው፡፡ በቢሊዮን ዶላሮች በሚገመት የበጀት ምደባ የማያገኙትን ከፋፋይ የትግል ሥልት በመከተላችን ወያኔዎች እኛን በጅልነታችን እንደሚያመሰግኑን አልጠራጠርም፤ በዚህ ረገድ ያጠመዱት ወጥመድ ተሳክቶላቸዋልና በጣም ዕድለኞች ናቸው፡፡

እውነቱን ለመናገር ብዙ አክራሪነት ይታየኛል፡፡ አክራሪነት ደግሞ ያለያያል እንጂ ወደ አንድ የጋራ መድረክ አያመጣም፡፡ ሕዝቡ በተለይም ወጣቱ ሰከን ማለት አለበት፡፡ አንድን የዘር ሐረግ ብቻ እየነቀሱ በዚያ ላይ ማጠንጠን መጨረሻ ጥፋት መሆኑን መገንዘብ ተገቢ ነው፡፡ ከወያኔ ካልተማርን ፈጣሪ ራሱ ወርዶ ወንበር ዘርግቶ አያስተምረንም፡፡ “ኦሮሞና ዐማራ አንድ ሆኑ፤ ሌሎች ጎሣዎችንም በኅብረት አስተሳስረውና አማክለው ለሀገራዊ ነፃነት ፈር ቀዳጅ የጋራ ትግል ጀመሩ” ተብሎ ከመነገሩና በብዙዎች ዘንድ ከመወደሱ በሰሞኑ የእሬቻ በዓል አከባበር ላይ የታዘብነው ሁሉንም የማያካትትና ብዙኃንን ትቶ የአንድን ንቅናቄ ዓላማ ብቻ የሚያቀነቅን የትግል አቅጣጫ ትኩረት ሳቢ ነበር ማለት አይቻልም፡፡ ከስሜት ካልወጣን፣ ከጎጠኝነት ወይም ከክልላዊ የተናጠል ሩጫ ካልታቀብንና ለወል ማንነታችን ካልተጋን የጠላቶቻችን መሣሪያ እንደሆንን እንዘልቃለን፡፡

የማየው አክራሪነት ዘር ላይ የተመሠረተ ነው፡፡ ብዙ ወጣቶች ኦሮሞን ከኢትዮጵያ ገንጥለው የወያኔን አጀንዳ ለማራመድ ሲሞክሩ ይታያል፤ የፈረደበትን ወያኔ ልጥቀስ እንጂ ከወያኔ በማይተናነስ የዘውገኝነት አረንቋ ገብተን ዳግም እንድንዳክር የሚያስገድድ በዘረኝነት አባዜ የተለወሰ ድግስ የሚደግሱልን ወገኖች ሊኖሩ እንደሚችሉ በዚህ አጋጣሚ ባስታውስ ነውር ያለበት አይመስለኝም፡፡ እንደነዚህ ዓይነት ወገኖች ሃሳባቸው በተለያዩ ከፋፋይ ድርጊቶች ይገለጻል፡፡ ወልጋዳው አካሄድ ተጠናክሮ የሚታየው በውጪ ሀገራት በተለይም እንደልብ በሚፈነጩበት በዲያስፖራው አካባቢ ቢሆንም በተለይ ከቅርብ ጊዘያት ወዲህ ይህ ወረርሽኝ ወደ ሀገር ውስጥም ገብቶ ስሜት ቆንጣጭ በሆነ ሁኔታ እያቃቃረን ይገኛል፡፡ ልብ ልንገዛና ወደኅሊናችን ልንመለስ ባለመቻላችን ሌላው ሁሉ ቀርቶ የእግዚአብሔርን ቤት እንኳን በዘርና በጎሣ እየከፋፈልን “የአቡነ አረጋዊ ቤተ ክርስቲያን”፣ “የአቡነ ተክለ ሃይማኖት ደብር” ወዘተ. በሚል የመንግሥተ ሰማይንና የገሃነመ እሳትን ነዋሪዎች ሳይቀር በሣቅ የሚያፈነዳ ከንቱ የማይም ትያትር የምናሳይ “ኢትዮጵያውያን” ሞልተናል፡፡ እዚህ በሀገር ቤት መቼም ከመኪና ታርጋ ጀምሮ እስከ ባንክና ሌሎች የንግድ ተቋማት ድረስ በዘር ልምሻና በፆታና ሃይማኖት ድልድል ተኮድኩደን “ወጋገን ባንክ”፣”አንበሣ ባንክ”፣ “አዋሽ ባንክ”፣ “ዳሸን ባንክ”፣ “ንብ ባንክ”፣ “ብርሃን ባንክ”፣ “እናት ባንክ” … እያልን ስንጃጃል የሚታዘበን ቢኖር የአሣራችን ብዛትና የቂልነታን መጠን ዳር ድንበር የሌለው መሆኑን በግልጽ ይረዳል፡፡ ዘመን ሲያልፍ የምናወራው ስንትና ስንት የነውር ሥራ አለን መሰላችሁ፡፡

ሰሞኑን ከታዘብኳቸው እንከኖቻችን ጥቂቶቹ፡-

ትዝብት አንድ – አረንጓዴ፣ ቢጫና ቀይ የኢትዮጵያ ባንዴራ የዐማራ (ብቻ) አይደለችም፡፡ ይህች ባንዴራ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ኦሮሞዎችና ዐማራዎች እንዲሁም ትግሬዎችና ሌሎች ጎሣዎች በመላዋ ሀገራችን ከውጭ ወራሪዎችና ከውስጥ ምንደኞቻቸው ጋር በተካሄዱ ጦርነቶች ያለቁላት የቀስተ ደመና ምሳሌ ናት፡፡ ይህች ባንዴራ ለተንኮል ሲባል ቤተ ሙከራ ውስጥ ተፈልስፎ እንደሚሰጥ ዘመን ወለድ የጠላት ፍብርክ ባንዴራ ሳትሆን እነአባመላ ዲነግዴ፣ እነጄኔራል ደምሴ ቡልቶ፣ እነቀ.ኃ.ሥላሴ፣ እነመንግሥቱ ኃ.ማርያም፣ እነደጃች ገረሱ፣ እነጄኔራል ጃጋማኬሎ፣ እነአብዲሣ አጋ፣ እነ ስንቱን የኦሮሞ ጀግና አንስቼ ልዝለቀው – እነዚህ ሁሉ የኦሮሞ የጦር አበጋዞችና የሀገር መሪ ነገሥታት የተዋደቁላት ባንዴራ ዛሬ ለአንድ ጎሣ – ለዐማራ – በችሮታ ተሰጥታ በዚህ የተገፋ ሕዝብ ስም ስትጎሳቆል ማየት ከማሳዘኑም በላይ የታሪክን ፍርድ የሚጋብዝ ከፍተኛ ጥፋት እንደመፈጸምም ይቆጠራል፡፡ የሕዝብን የጋራ አንጡራ ሀብት ቀምቶ ለአንድ ነገድ ብቻ ማስታቀፍ ነውርና ጣሪክን አለማወቅ ወይም ጨርሶ መካድ ነው፡፡ ይህ በዘመን የሾመጠረ ጠላ ሰክሮ እምቡር እምቡር ማለት ደግሞ የትም እንደማያደርስና ውሉን የማይስተው ታሪክ ትክክለኛ መስመሩን ሲይዝ ለትዝብት እንደሚዳረግ መረዳት ተገቢ ነው፡፡ ሸረኛ ሰዎች በዘረጉት የወጥመድ ጉድጓድ ውስጥ ገብቶ በስሜት ስካር ከመጨፈር ይልቅ ወደ እውነተኛው ታሪካችን በመመለስ በወያኔ ሤራ የላሉና የተበጣጠሱ የአብሮነታችንን ገመዶች ማጠባበቅ ይሻለናል፡፡ ስሜትና እውነት እንደሚለያዩ ካልተገነዘብን ዘመን ወለድ ስካራችን በቀላሉ አይለቀንም፡፡

ስለሆነም ወደኅሊናችን በመመለስ የጥንት የጧትን አእምሯዊና ባህላዊ የጋራ ሀብትና ንብረት አክብሮ መያዝ ይኖርብናል፡፡ ንፋስ ወደነፈሰበት ሁሉ እየዞርን አንገታችንን ማጣት አይገባንም፡፡ በአንድ በኩል ኅብረትና አንድነት ፈጠርን እያልን በሌላ በኩል የጋራ ሀብታችንን መጥላትና ወደ አንድ ጎሣ መለጠፍ ተገቢም ወቅታዊም አይደለም፡፡ በአንድ ጊዜ ሁለት መሆን አይቻልም፡፡ ለመሠሪዎች ተንኮል መንበርከክም ለተራዘመ የግፍ አገዛዝ ከመዳረግ ውጪ አንዳችም ፋይዳ የለውም፡፡ ከጎጂ መሠረት አልባ እልህ ወጥቶ ምክንያታዊና ሰብኣዊ ፍጡር መሆን ይገባል፡፡ በኦሮምኛ ትውፊት “ትናንት አልፏልና አያስጨንቅህ፤ ነገም ያንተ ላይሆን ይችላልና እጅግም አያሳስብህ፤ ዛሬ ግን በእጅህ ያለ በመሆኑ በጥበብና በማስተዋል ተጠቀምበት” የሚል በሳል ብሂል አለ፡፡ ብልኆች ይህን ብሂል አጢነው በአግባቡ ይጠቀሙበታል፤ ዝንጉዎች ግን በሰው አልባሌ ምክር እየተወሰዱ ጊዜያቸውንና አቅማቸውን በሞላ ለአሉታዊ ዓላማና ግብ ያውሉታል፤ በመጨረሻው ግን ለፀፀት መዳረጋቸው አይቀርም፡፡

በደብረ ዘይት ዕልቂት የኢትዮጵያን ንጹሕ ባንዴራ ብመለከት ኖሮ ደስታየ ወሰን ባልነበረው፡፡ የወያኔን ባንዴራና ከፋፋይ ወገኖች የደረቱልንን ቡትቶ አስወግደን በመጣል ከፍ ሲል የጠቃቀስኳቸውና ሌሎች ኢትዮጵያውያን ወገኖቻችን የተሰውላትን ንጹሕ አረንጓዴ ቢጫ ቀይ ሰንደቅ ዓላማ ብንሰቅል ኖሮ ትግላችንን በሰማንያው የኢትዮጵያ ነገድና ጎሣ ሁሉ ልናስደግፈው በቻልን ነበር፡፡ ሰይጣን ይሁን ወይም ወያኔዊ የዓመታት መርዘኛ ፕሮፓጋንዳ ያን ብልኃትና ጥበብ ሰውሮብን ለሕዝብና ለመሬቱ ባዕድ የሆነ ሌላ ባንዴራ በማሳየታችን ትግላችንን አሳነስነው፤ የሌሎችንም ድጋፍ አቀዘቀዝነው፡፡ ተገቢ አይደለም፡፡ በውጭ ሀገር በሚደረጉ ሰልፎችም ይሄው አዲስ ክስተት ይታያል፡፡ በስመ “እነእንትናን ላለማስቀየም” ሲባል እርጥብን ከደረቅ፣ ነጭን ከጥቁር መሞጀር አግባብ አይደለም – እውነቱን ልቦናችን እያወቀው – የልቦናችንን ማወቅም ሁሉም ወገን እየተረዳው አጉል መሸዋወድ ተገቢ አይደለም፡፡ ያለህን የጋራ ንብረት በመጣል አይደለም ማንነትህን የምታስጠብቀው፤ ያልነበረህን በነበረህ በመለወጥና አዲስ ማንነት በመደረት አይደለም ፍቅርና አንድነት የምታዳብረው፡፡ “ያልወለድኩት ልጅ ቢለኝ አባባ፤ አለው አፌን ዳባ፣ ዳባ” ይባላል፡፡ “የራስህ ጉዳይ ነው” እንዳትሉኝ እንጂ ለምንድን ነው እኔ የብኣዴን ተብዬውን ባንዴራ ከነቀለሙ እንኳን እስካሁን ላውቀው ያልቻልኩት? ማንም እየተነሣ የላዩ ላይ በል ባለው ቁጥር ባንዴራ እየጠፈጠፈ በየአምሳና መቶ ዓመቱ የሚያሸክመኝ ነፈዝ ከሆንኩ ምኑን ሰብኣዊ ፍጡር ሆንኩት! እንደዚያማ ከሆንኩ የኔን ነፃነት፣ የማሰብና የማገናዘብ ችሎታየን ምን ወሰደብኝ ሊባል ነው? አሜሪካውያንን ተመልከት፣ እንግሊዛውያንን ልብ በል፡፡ ማንም ሞቅ ያለው የጨረቃ ሌሊት ዕብድ ሁሉ እየመጣ ባንዴራን አይለውጥም፤ ሀገር እንደማይለወጥ ሁሉ የጥንት አባቶችና እናቶች የሞቱለት ሰንደቅ ዓላማም ግርግር በተፈጠረ ቁጥር አይቀየርም፡፡ ለዚህም ነው በባንዴራ የሚደረግ ድርድር ቅጥ ያጣ ድርድር የሚሆነውና ሰውን አስደሰትኩ ብለህ የጋራ ማንነት መገለጫህን ዋጋ ማውረድ የማይገባህ፡፡ ይታሰብበት፡፡

ማለባበስ ይቅር የምለው እንግዲህ ከነዚህ መሠረታዊ ነጥቦች በመነሳት ነው፡፡ ይህን ጉዳይ በሚመለከት ከብዙዎች ኦሮሞዎችና ሌሎች ጓደኞቼ ጋር ስንጨዋወት የተረዳሁት ሃቅም ይሄው ነው፡፡ ትግላችን እንዲሰምር ከታይታዊ የይስሙላ መተባበር ይልቅ ለእውነተኛ የመተማመንና የመዋደድ ስሜት መገዛት አለብን፡፡ ትብብራችን የስትራቴጂ ወይም የሥልት ከሆነ ቀደም ሲል እንደተናገርኩት አለባብሶ ማረስና ለዐረም ሲመለሱ መቸገር ነው፤ ማኅበራዊ ዕርቅና ስምምነት ግልብ ሳይሆን ልባዊ መሆን አለበት፤ የሚያስተማማና እየቆዬ የሚያመረቅዝ ነገር መኖር የለበትም፤ የሚያሸምቁበት ሸፍጥም ሊኖር አይገባም፤ ፍጹማዊ መግባባትና ግልጽነት በተስማሚዎች መካከል ሊሠፍን ይገባል፡፡ የዛሬ ዐርባና ሃምሳ ዓመት ያልነበረ ነገር ዛሬ መጥቶ የዛሬ ዐርባና ሃምሳ ዓመታት የነበሩ ፍጡራንን ሊከፋፍልና የሚደርስባቸው በደልና ጭቆና ላይ ልብ ለልብ ተገናኝተው እንዳይታገሉ ደንቃራ ሊፈጥርባቸው አይገባም፡፡

“ትናንት እገሌ ገዝቷል፤ ዛሬ እነእገሌ እየገዙ ነው፤ ዛሬ ደግሞ እኛ እንግዛ” የሚሉት አስቂኝ ፈሊጥ ደግሞ በጭራሽ አያዛልቅም – ይህ ሥልት በዚህ በምንገኝበት የዴሞክራሲ ዘመን ለመታገያና ለማታገያነት ቀርቶ ሊሰሙት የሚያሰጠላ ያረጀ ያፈጀ ሥልት ነው፡፡ በመሠረቱ ማንም ቢገዛ ለዘመዶቹና ለጥቂት ወገኖቹ የሀብት መንገድ ይከፍት እንደሆነ እንጂ በቋንቋና በዘር ምክንያት ሁሉም አያልፍለትም፡፡ ይህ ቢሆን ኖሮ እንደትግሬ ወያኔ ዘረኛ እንዳለመኖሩ አዲስ አበባ ላይ የሚለምን አንድም የትግሬ ጎሣ አባል ባልነበረ፡፡ የአዲስ አበባን መንገዶች ሁሉ ተመልከቱ – ከትግራይ የመጡ የኔ ቢጤዎች እንደማንኛውም ጎሣ አባላት እየለመኑ ታገኟቸዋላችሁ፤ ከጠቅላላው የተጋሩ ብዛት አኳያ ያለፈለት ትግሬ ጥቂት ነው፡፡ ያላለፈለትና እንደኛው እንደብዙዎቹ መከራውን የሚበላው ትግሬ ብዙ ነው፡፡ እርግጥ ነው – እንደዬግለሰቡ አእምሯዊ ጥንካሬ የሚታይ ሆኖ አብዛኛው ወይም በጨዋ አነጋገር ጥቂት የማይባለው ትግሬ ችግሩን በሥነ ልቦናዊ ኩራት ሊያስታምምበት የሚያስችለው ብዙዎቻችን በወቅቱ በግልፅ ይታያል ብለን የምናምነው ትግሬያዊ የበላይነት የሚፈጥርለት ባዶ ተስፋ ሊሰንቅ ይችል ይሆናል፡፡ ተስፋ ግን ሆድን አይሞላምና የመንደሬን ነዋሪ ወይዘሮ አብረኸትን ከአምባሻ ሻጭነት ወይም ወጣት ግደይን ከቁራሌነት አውጥቶ ባለፎቅ ያደረገ ትግሬ ወያኔ እስካሁን አላገኙም – እውነቴን ነው፤ ረጋ ብለን ከታዘብን ስሜትና እውነት እንደሚለያዩ ማጤን እንችላለን፡፡ ስለሆነም ይህ በዘር ላይ የተመሠረተ የአገዛዝ እሳቤ ልቦለዳዊ እንጂ እውናዊ አይደለም፡፡ እናም ወደ አቅላችን እንመለስ፡፡ ደግሞም የአሁኑን የወያኔ አገዛዝ ለታሪክ ፍርድ ትተን ለጊዜው እንርሳውና የዱሮዎቹን አገዛዞች ብናይ ያን ያህል በዘርና በጎሣ የተመሠረቱ ናቸው ብለን የምንወቅሳቸው እንዳልነበሩ ጤናማ ኅሊና ያለን በዕድሜ አንጋፋ ሰዎች የምንፈርደው ነው፡፡ ኢትዮጵያ ውስጥ የለየለት ዘረኝነት የታየው አሁን እንጂ የቀድሞዎቹ እኩል ይገድሉን፣ እኩል ይቀጠቅጡን፣ እኩል ይጨቁኑንና ያንላቱን ነበር እንጂ ለአበበና ለደቻሳ ወይም ለዘበርጋና ለሐጎስ በሚል የተለዬ ሕግ አውጥተው ከፈሪሃ እግዚአብሔር መንገድ የሚያፈነግጡ አልነበሩም፡፡ ባልነበረ ነገር አንኮነን፡፡

ትዝብት ሁለት ፡- ቋንቋን በሚመለከት ደግሞ ጥቂት የምለው ነገር አለኝ፡፡ ዐማርኛ መናገር የሚችል ኦሮሞ ዐማርኛን መናገር ለምን ይጠየፋል? የቋንቋና የሰው ግንኙነት እኮ የመራጃና የሰው ግንኙነት እንደማለት ነው፡፡ ቋንቋ ማለት እንግሊዝኛም በለው ቻይንኛ ወይም ዐማርኛም በለው ኦሮምኛ ከአንድ ዶማ ወይም ከአንድ ማረሻ አይለዩም፡፡ በቃ፡፡ ልዩነቱ – ልዩነት ከተባለ – ዶማው ለመቆፈሪያነት ሲውል ቋንቋው ደግሞ ለመግባቢያነት ማገለልገሉ ብቻ ነው – አንዱ ይታያል ሌላው አይታይም፤ አንዱ ቁሣዊ ነው ሌላኛው ረቂቅ የአእምሮ ሥሪት ነው፡፡ ከዚያ ውጪ “ያንተ ቋንቋ፣ የኔ ቋንቋ” በሚል ይህን ያህል ልንወራከብበትና በሥነ ልቦና ልክፍት ተጠምደን ልንፋጅበት የሚገባን አይደለም – በዚህ ረገድ ብዙ አለማወቅና ብዙ የስሜት መነዳት ይታያል፡፡ እንደኔ ቢቻል ሁላችንም ኦሮምኛ ብንችልና በርሱ ብንጠቀም ደስ ባለኝ፡፡ እንደታሪክ አጋጣሚ ሆኖ ግን ሰማንያው የኢትዮጵያ ጎሣ የሚግባባው በዐማርኛ ሆነና ቋንቋው ለራሱም ዐማርኛ ቋንቋ ተናጋሪ ለሚባሉትም ጥላቻን አትርፎ ቁጭ አለ – ምሥጋናና ወሮታ ማስገኘት ሲገባው፡፡ አንዳንድ ዕቃ ሳትወድ በግድ ዕዳ ያመጣብሃል፤ አንዳንድ ዕቃ ደግሞ ሸጠኸውም ሆነ አከራይተኸው ወይም አውሰኸው ጥቅም ታገኝበታለህ፡፡ ዐማርኛ ግን ለዐማሮች ያስገኘላቸው የዕልቂት ዐዋጅ ሆነ፡፡ የበሉበትን ወጪት መስበር መቼም እንደኢትዮጵያውን የሚያውቅበት የለም፡፡ …

ዐማርኛን በጋራ መግባቢያነት መጠቀም ካልፈለግን ደግሞ ከሌሎቹ አንዱን እንምረጥና እንጠቀምበት፡፡ በጎች እንኳን ሲቀላቀሉ “እምባ” ይላሉ፡፡ እኛ ደግሞ ሰዎች ስለሆንን ስንገናኝ አንድ ወይ ሁለት እንዳስፈላጊነቱም ከዚያ በላይ የወል መግባቢያ ያስፈልገናል፡፡ ዐማርኛ በታሪክ አጋጣሚ ይህን ቦታ ሊያገኝ ቻለ እንጂ ቀደምት ተናጋሪዎቹ ወረፋ ይዘውና ከንጉሥ ደጅ ጠንተው ይህን የመከራ ዕጣ ፋንታ የተቀበሉ አይመስለኝም፡፡ ታዲያ ለምን እንጠየፈዋለን? ሰዎቹንስ ባልሠሩት ሥራ ለምን እንጠላቸዋለን? ሌላ የተሻለ አማራጭ እስክናገኝ ብንጠቀምበት ምን እንጎዳለን?

አስፈላጊ ሆኖ ካገኘነው ቋንቋውን ይናገሩታል የሚባሉ ሰዎችን ግዴለም እንራቃቸው – ይህም ስህተት መሆኑ እንዳለ ሆኖ፡፡ እነሱን መጥላትና የነሱ ስለመሆኑ እንኳን በወጉ የማይታወቀውን ዐማርኛን መጥላት ግን ስህተት ነው ብቻ ሣይሆን ጤናማነት የሚጎድለው የተዛባ አመለካከት ነው፡፡ ባሏን የጎዳች መስሏት ስስ የሰውነቷን ክፍል በጋሬጣ እንደቧጨረችው ሴት መሆን ይቅርብን፡፡ ለምሳሌ ኦሮሞና ዐማራ ተባበሩ በተባለበት ማግስት እንኳን “በእናቴ ዐማራ ነኝ” የሚለው ሣተናው የባህር ማዶ ታጋይ ዐማርኛን ሲጠየፍ ይስተዋላል፡፡ ለምን? ዐማርኛ ቋንቋ ሁሉንም የኢትዮጵያ ነገዶችና ጎሣዎች አስተባብሮ ባንድ ግዛት ውስጥ ተቻችለው እንዲኖሩ ማድረጉ ስህተት ይሆን? ይህ ዓይነቱ ጠባይ በቅጡ ካልተያዘ ጠባብነት የሚመነጭ ሲሆን በሌላም ወገን የቋንቋን ተፈጥሯዊ የኢ-ባህያዊነት ጠባዩን ካለመገንዘብ የሚመጣ ነው፡፡ ቋንቋና ሸሚዝ አንድ መሆናቸውን ለሚረዳ ለእንደኔ ዓይነቱ ሰው ግን ሰዎች እንኳንስ በሰዎች ቋንቋ በዝንጀሮ “ቋንቋ”ም ቢግባቡ ድንቅ ነገር እንጂ አያስከፋም፡፡… ይህቺ በቋንቋ ምክንያት ቱፍ ቱፍ የሚሉ ሰዎች በስስ ሰብኣዊ ጠባይ በመግባት መሰሎቻቸውን ወይም ቢጤዎቻቸውን በቀላሉ በማስቆጣት ለሚፈልጉት ዓላማ ለማነሳሳት እንጂ በርግጥም የቋንቋ ጉዳይ ያን ያህል ሚዛን የሚደፋ ሆኖ እንዳልሆነ ሳይገባቸው ቀርቶ አይመስለኝም፡፡

በነገራችን ላይ አንድ ቋንቋ ለብዙኃን የወል መግባቢያነት እንዲውል ሲደረግ ቋንቋውን በአፍ መፍቻነት የሚጠቀሙት ሰዎች ቁጥር ከቁብ አይጣፍም፡፡ እንደዚያ ቢሆን ኖሮ በአሁኑ ሰዓት የኢትዮጵያ የጋራ ቋንቋ ከምኞት ባለፈ ትግርኛ ሊሆን በቻለ ነበር፡፡ የዓለም ቋንቋ ደግሞ መንደሪን የሚባለውና ከአንድ ቢሊዮን ሕዝብ በላይ የሚገመት ቻይናዊ የሚናገረው ቋንቋ በሆነ ነበር፡፡ ምሥጢሩ ያለው ቋንቋው በድልድይነት ስንቶችን ያገናኛል? የሚለው ነው እንጂ “ስንቶች በአፍ መፍቻነት ይናገሩታል?” የሚለው አይደለም፤ ይህን እውነት አለማወቅ ለቋንቋ አርበኝነት በማጋለጥ ላልተፈለ ኩርፊያና ላልተጠበቀ ጉዳት ይዳርጋል፡፡ ኅብረ ብሔራዊ በሆኑ የኛን መሰል ሀገራት ውስጥ አንድ ቋንቋ ለጋራ ቋንቋነት የሚመረጠው “ከራሴው ውጪ የማንንም ቋንቋ አልጠቀምም” በሚል በርህን በመጠርቀም ሣይሆን “የትኛው ቋንቋ በየትኞቹ ማሕበረሰቦች ዘንድ በስፋት ይነገራል?” የሚል ጥናት በመመርኮዝ ነው፡፡

ዐማርኛን ለመግደል ብለው ወያኔ ትግሬዎች ብዙ ሠሩ፤ በሥልጣን ቆይታቸው የዐማርኛን ጥቅም በሂደት ሲረዱ ግን ዐማሮችን የማጥፋት ዋና ተልእኳቸውን ለአፍታም ሳይዘነጉ ቋንቋውን ነጥለው ለልጆቻቸውና ለካድሬዎቻቸው በደንብ ማስተማሩን ተያያዙት፡፡ እነሱ አካሄዳቸውን ሲለውጡ ሌላው የነሱን የቀደመ ፈለግ ተከትሎ ዐማርኛን ሲጠየፍና ሲያንቋሽሽ ቆይቶ በመጨረሻው ሲያጤነው አዲስ አበባ የገቡት ልጆቹ የዘበኝነትና የጽዳት ሥራ ለመያዝ እንኳን መቸገራቸውን ተገነዘበ፤ በዲግሪ ተመርቀወም አዲስ አበባ ሲመጡ ወይ እንግሊዝኛ አልቻሉ ወይ ዐማርኛ አልቻሉ ከሁለት ያጣ ጎመን እየሆኑ መቸገራቸውን ሲገነዘቡ በወያኔ የመበለጥ ሞኝነታቸውን በማሰብ አምርረው አዘኑ፡፡ ይህ ነው እንግዲህ አንዱ የወል ቋንቋ ዕንቆቅልሽ – ቋንቋውንና ተናጋሪዎቹን የመጥላትና የመውደድ ጉዳይ አይደለም ወንድሜ፡፡ ስለዚህ በምናውቀው ልሣን ሁሉ እንግባባ እንጂ የኩራት ድንበር አናብጅ፤ አንተ በዐማርኛ ላይ አፍንጫህን ብትነፋ ዐማርኛ አይጎዳም፤ አንቺ በትግርኛ ወይም በኦሮምኛ ላይ ፊትሽን ብታዞሪ እነሱ ግዑዛን ናቸውና አይጎዱም፡፡ ቋንቋ የትም ብትሄድ ወስፋትህን የምትሸነግልበት የእስትንፋስህ መሠረት የሆነ የመግባቢያ መሣሪያ እንጂ ጠላትህ ሊሆን አይችልም፡፡ ያን ቋንቋ በአፍ መፍቻነት ማንም ይናገረው ማን ላንተ ያለው ጠቀሜታ ግን ከምንም በላይ ነው፡፡ ዓለም ወደ አንድ መንደርነት እየተለወጠችና አንድነቷን እያጠናከረች በምትገኝበት የግሎባላይዜሽን ዘመን በራስህ ጠባብ ዓለም ውስጥ በምትፈጥረው ምክንያት የተነሣ ለዚህና ለዚያ ቋንቋ ያለህ አተያይ ቢንሻፈፍ ተጎጂው አንተው ብቻ ነህ፤ ኩራት እራት መሆኑ ቀርቷል ወዳጄ ልቤ – (እንደቃና ቲቪ ‹ወዳጄ ታየር› ልበልህ ይሆን?)፡፡ በወያኔ የቋንቋ ፌዴሬሽን ሳቢያ ስንቶች እንደተጎዱ እኔ ነኝ የማውቀው – መምህር ነበርኩና፡፡

ስለዚህ ግዴላችሁም ሌላ የምንተካው እስክናገኝ ድረስ ለጊዜው በዚሁ ቋንቋ – ባማርኛ – እንጠቀም፡፡ በማይጨበጥ ምክንያት በጠላቶቻችን ተገፋፍተን ልንሰባብረው የሞከርነውን ማኅበረሰብኣዊ ድልድይ በአፋጣኝ እንጠግን፡፡ አለበለዚያ እየሞትን ነው፤ እግዜር አይበለውና በጠላቶቻችን ምክርና ሰይጣናዊ አስተምህሮ ከቀጠልን የሁላችንም ወረደ መቃብር በአጭር ጊዜ ውስጥ ይፈጸማል፡፡ የመከፋፈላችን ብሥራት ለጠላቶቻችን የደስታ ምንጭ ነው፡፡

“አገባሻለሁ ያለ ሁሉ ላያገባሽ ከባልሽ ጋር ሆድ አትባባሽ” የሚለውን የዐማርኛ ብሂል “ይበጃል ቢሉን አህያ አረድን፤ አይበጅም ቢሉን ጠራርገን ጣልን፤ ‹(የአህያው ሥጋ) ይበጃችሁ ነበር እኮ› ቢሉንና ሄደን ብንፈልገው አጣነው” የሚለውን የኦሮምኛ ብሂል እንድታጣጥሟቸው በመጋበዝ ልለያችሁ፡፡ ለሁላችን መልካም ክራሞት፤ ለሀገራችንም ሰላምንና በአዲስ ሕዝባዊ ኢትዮጵያዊ መንግሥት ሥር መረጋጋትን ተመኘሁ፡፡

የኦሮሚያ የሽግግር መንግስት ? የኦሮሚያ መከላከያ ስራዊት በርግጥ ታስቧልን ? አቶ ጀዋር ሙሃመድ እና ፕሮፌሰር ህዝቄል ጋቢሳ በጋዜጠኛ ሳዲቅ አህመድ ይጠየቃሉ

ከአርባ ምንጭ ወደ ጨንቻ ወረዳ 48 ሰዎችን የጫነ የህዝብ አውቶብስ ለተቃውሞ በወጡ ሰዎች ተቃጠለ

0
0

ጃዋር መሐመድ

በዛሬው እለት በቀን 27/1/09 ዓ.ም ከሰአት 8፡30 ከአርባ ምንጭ ወደ ጨንቻ ወረዳ 48 ሰዎችን የጫነ የህዝብ አውቶብስ ለተቃውሞ በወጡ ሰዎች ተቃጠለ ። በአደጋው ሰው ላይ አንዳችም ጉዳት አልደረሰም።ነገር ግን ይህ ተቃውሞ በከተማዋ እየተዛመተ ይገኛል
“ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ”

14485029_10102585299530813_8262737888164949382_n
jawar

‘‘ብርሌ ከነቃ ፥ ኣይሆንም እቃ’’ (ከኣረጋዊ በርሀ)

0
0

ይድረስ ለህወሓት/ኢህኣዴግ ቱጃሮች፣ ኣባይ ጸሓየ፥ ስዩም መስፍን፥ ኣጃቢዎቹ ኣባዱላ ገመዳ፥ በረከት ስምኦን፥ ካሱ ኢላላና የገዢው መደብ ኣባላት!
‘‘ብርሌ ከነቃ ፥ ኣይሆንም እቃ” የሚል የኣበው ኣባባል ኣርቆ ለሚያስብ ሰው በቂ መልእክት በሆነ ነበር፣ ታዲያ ለኣርቆ ኣሳቢነት ስላልታደላችህ እንደፈረደብኝ ዝርዝር ውስጥ መግባት ግድ ይሆንብኛል። መልእክቴ በሶስት ጉዳዮች ላይ የተካተተ ነው።
1 ኛ/ የቀየሳችሁት የጨለማ መንገድ
2 ኛ/ የፈጠራችሁት ኣጠቃላይ ቀውስ እና
3 ኛ/ ከቀውሱ ኣዙሪት መውጫው የሚመለከቱ ናቸው።በጥቅሉ ሲታይ የኣገዛዝ ንድፋችሁ የኢትዮጵያን ጥንታዊ፥ ማእከላዊና ዘመናዊ ታሪክ ያላገናዘበ፣ በማህበረ-ኢኮኖምያዊ ጥናት ያልተደገፈ፥ ስልጣንን በኣፈሙዝ መያዝ ብቻውን ዋናው ዓላማ ያደረገና የህዝብን ሓያልነት በጠብመንጃ ሊገዛ ያቀደ ደንባራ ትልም ነው ማለት ይቻላል። ይህ የጨለማ ዝላይ ሃገራችንን ዘመነ-መሳፍንትን ከሚያስንቅ ውስብስብ ቀውስ ውስጥ ከትዋት ይገኛል። በይበልጥ የሚያሳዝነው ደግሞ ይህእዚህ ያደረሰንን ጨለምተኛ ጉዞ ኣሁንም ልትቀጥሉበት ማቀዳችሁና ለዚሁ ተብሎ የንጹሃን ደም በገፍ ማፍሰሳችሁ ነው። እዚህ ያደረሰን ዕቅዳችሁ ግድ ብሎ፥ ኣሁን እማያላውስ ሙት-ቦታ መድረሱና ከዚህ ኣጣብቂኝ በሰላም መላቀቅ የመላው ኢትዮጵያ ህዝብ የማይቀለበስ ወቅታዊ ጥያቄ መሆኑ ይታያችሁ ይሆን? ታያችሁም ኣልታያችሁ፥ የሰላሙን መንገድ ኣልቀበል ካላችሁ የኣመጽ ማዕበል ቀጣይ ነው።ለነገሩ ብርሌው የነቃ ከጅምሩ ነው። ገና ስልጣን ላይ ሳትወጡ ጸረ-ኣንድነት የሆነውን የመገንጠል ኣባዜ ታራምዱ ነበር። የለም! የተነሳንበት ዓላማ ብሄረሰቦችዋን እኩል የምታስተናግድ ዴሞክራሲያዊት ኢትዮጵያ ስለሆነ መገንጠልን ወጊድ በሉ በማለት የተቃወምዋችሁን በሰበብ ኣስባቡ ስትገድሉ፣ ስታስሩ፣ ስታሳድዱና ያልሆነ ስም ስትቀቡ ኖራችሁ። የመገንጠሉ ደባ በሁሉም ዘርፎች ላይ ሲንጸባረቅ፥ በተለይ በባህር- በር ጥያቄእና በስልጣን ክፍፍል ጉዳይ ላይ ጎልቶ በመታየቱ ሃገር-ኣቀፍ ተቃውሞ ኣስነሳ። ከጉዳይ ኣልቆጠራችሁትምና ከህዝቡ ጋር ሆድና ጀርባ፣ እሳትና ጭድ ሆናችሁ ዘለቃችሁ። ኢትዮጵያ የባህር በር መብትዋ ይከበር ብለው ድምጻቸውን ያሰሙ ሁሉ በጥይት ከመደብደብ ኣልፎ “ኢትዮጵያ ባህር በር ኣልነበራትም፣ ኣይገባትም” በማለት ተሳለቃችሁ / ኣፌዛችሁ። ሰላማዊ ተቃውሞ ባሰሙ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ስነ-ሞገታዊ መልስ መስጠት ስላቃታችሁ የጥይት ናዳ በመልቀቅ ብዙዎቹን ፈጃችሁ። ስልጣን ላይ ለመሰንበት ተቃዋሚን መግደል፥ ማጥፋት፥ ኣስሮ ማሰቃየት እንደ ዋና ኣሰራር ስለወሰዳችሁት ኣሁን ድረስ ትጠቀሙበት ኣላችሁ። ይህ ሃገራዊ በደል ተከትሎ የሙስናው፣ የመጥፎ ኣስተዳደሩ፣ የመሬት ቅሚያው፣ የሓሳብ መግልጽና የእምነትነጻነት ኣፈና፣ የስውር ግድያው በደሎች ኣነገሳችሁ። በርግጥ መቃወም መብት እንደሆነ ቢገባችሁ ኖሮ እስካሁን ድረስ በተፈወሳችሁ ነበር፣ ካሁን ወድያ ይገባችሁ ይሆናል ብሎ መገመት ደግሞ ከየዋህነት ኣልፎ ቂልነት የሚያስብል ቢሆን ነው። የመብት ጥያቄ የሚያነሳ ንቁ ዜጋ ሁሉ በጠላትነት፥ በኣሸባሪነት፥ በከሃዲነት ፈረጃችሁት። ገዢ ቦታ በጉልበት ስለተቆጣጠራችሁ መብት የናንተ ብቻ ሆነች። ኣምባገነንነት ይሉታል ይህ ነው። ለሁሉም ገደብ ኣለውና፥ ስቃዩና መከራው የበዛበት ህዝብ ኣሁን ጥይት፣ ዱላ፥ እስር ቤት፣ መፈናቀልን ሳይፈራ በቃኝ ብሎ ተነሳባችሁ።በዓለም ፊት ተጋለጡ ሲላችሁ፥ በ 100% ድጋፍ ሰጥቶን ምርጫ ኣሸነፍን ብላችሁ የዋሻችሁት መላው የኢትዮጵያ ህዝብ ነው የተነሳባችሁ።

[Must-Listen] Dr. Aregawi Berehe Answers Your Questionsበምርጫ ስርቆት ኣደባባይ ላይ ስትዋረዱ፥ ሓፍረተ-ቢስ ናችሁ እንጂ በሰለጠኑት ሃገሮች እንደሚደረገው፥ የውሸት ስልጣን በቃን ብላችሁ የሰረቃችሁት ስልጣን መልሳችሁ ማስረከብ ነበረባችሁ፣ ኣልያም እምነተ-ድምጽ (vote of condence) እንዲካሄድ ማድረግ ነበረባችሁ።ኣልሆነም፣ ኣይሆንምም። ለዚህ ዓይነቱ ዴሞክራሲያዊ ኣካሄድ ባእድ ሆናችሁ እንደቆያችሁት ባእድ ሁናችሁ ታልፋላችሁ። ለዚህም ነው “በጥልቀት እንታደሳለን” የሚለው የሰሞኑ ፈሊጣችሁ እንደ ስላቅም እንደ 2ጭንቀትም ሆኖ የሚታየው። በኣስርና መቶ ሺዎች ገድላችሁ፣ ኣስራችሁ፣ ኣደህይታችሁ፣ ለስደት ዳርጋችሁ፥ ከዚሁ ከለመዳችሁት እኩይ ኣሰራር ላትላቀቁ፣ ሺ ጊዜ ተሃድሶ ብትሉ ኣይሰራም፥ የበሰበሰ ኣዕምሮ ቁምነገር ኣይወጣውምና የለውጥ ሂደት ባታደናቅፉ ይሻላል። ስዩም መስፍን በተሃድሶ “ ከገባንበት ኣዘቅት በፍጥነት መውጣት ኣለብን – ኣለዚያ ኣወዳደቃችን ኣያምርም ” ቢልም ለ 25 ዓመታት የበሰበሰ ኣዕምሮ ኣሁን ይታደሳል ብሎ ማሰብ ከእባብ እንቁላል እርግብ መጠበቅ ሊሆን ነው። ይልቅስ ኣወዳደቃችሁ ብታሳምሩ ይሻላል እላለሁ። ይህን ስል ለናንተ ራርቼና በማይቀረው ውድቀታችሁ ኣዝኜ እንዳይመስላችሁ፣ ስትፈራገጡ በየቀኑ የምታጠፉት የሰው ህይወት፥ ከል የሚለብሱት ቤተሰቦች እና የሚወድመው የሃገር ሃብትኣሳስቦኝ እንጂ።ሰሞኑን በህዝቡ ማዕል ተደናግጣችሁ፥ ከተኛችሁበት የምቾት ወንበር ተቀስቅሳችሁ በሬድዮና ቲቪ የለቀቃችሁት የሰዓታት ልፈፋ በጣም ኣሰልቺና ኣሳፋሪ ነበር። ከዛ በላይ ደግሞ መሬት ላይ ካሉት እውነታዎችምንኛ እንደተራራቃችሁና ያለቀላችሁ መደባዊ ቱጃሮች መሆናችሁን ኮለል ኣድርጎ የሚያሳይ ነው። ወደ ዝርዝሩ መግባት ጊዜ ማባከን ስለሚሆን፥ ያዋጣናል ብላችሁ ደጋግማችሁ በምታነስዋቸው 2 ነጥቦች ላይ ብቻ ምላሽ ልስጥ፣ 1 ኛ/ “ሕገ መንግስቱ የኢትዮጵያ ህዝቦች መብት ያስከበረ ነው”።2 ኛ/ “እድገታችን የፈጠረው ችግር” ለወቅቱ ህዝባዊ ተቃውሞ መንሳኤ ሆነዋል፣ የሚሉ ናቸው።በመጀመርያ ደረጃ ሕገ መንግስት ማለት የኣንድን ሃገር መሰረታዊ ሕጎችና ኣቁዋሞች ያጠቃለለ፣ የህዝቡ ኣመኔታ የተጎናጸፈ፣ በተለይ ደግሞ የመንግስታዊ ኣካላት ስልጣንን የሚገድብ የበላይ ሕግ ነው። እናንት ግን እንደ ድርጅትም እንደ ግለ-ባለስልጣንም የሚያግዳችህ ሕግ ስለሌለ ሕገ መንግስት ኣለ ብሎ መናገር ኣይቻልም። ሕገ መንግስት እያላችሁ የምትመጻደቁበት ራሳችሁ ኣርቅቃችሁ የጫናችሁብን ቻርተር፣ ቆየት ብሎ ሕገ መንግስት የሚል ስም ተለጥፎበት በደጋፊዎቻችሁ የጸደቀ ድርጅታዊ ፕሮግራም ነው። ከኣቀራረጹም ከይዘቱም የህወሓት/ኢህኣዴግ ፕሮግራም እንጂ ሕገ መንግስት ለመሆን ኣይበቃም።የኢትዮጵያ ህዝብም እንደ ሕገ መንግስቱ ኣያውቀውም። ስለዚህ ህዝቡ በነጻነት ላላጸደቀውና እውቅና ላልሰጠው ቻርተር ወይም ‘ሕገ መንግስት’ ተገዢ መሆን ኣይችልም። ኣይጠበቅበትምም። ስለ ሕገ መንግስት ኣቀራረጽና ተኣማኒነቱ ፕሮፌሰር ተስፋጽዮን መድሃኔ የደረሱት ጥናታዊ ጽሑፍi ብታነቡ ፕሮግራማችሁን ኣጣጥፋችሁ በተቀመጣችሁ ነበር። ያም ሆኖ እናንት እራሳችሁ ሕገ መንግስት ብላችሁ ያረቀቃችሁትን ፕሮግራም እየጣሳችሁ ያሻችሁን ስታደርጉ፣ ህዝቡ እንዲያከብርላችሁ መጠበቃችሁ የለየለትኣምባገነንነት ኣልያም ጅልነት መሆኑን ብታውቁት ደግ ነው። ለመሆኑ ከሰነዱ ኣንቀጽ 10 ቁ. 1/2 ምን እንደሚል ታውቃላችሁ? 1. ሰብዓዊ መብቶችና ነጻነቶች ከሰው ልጅ ተፈጥሮ የሚመነጩ— የማይጣሱና የማይገፈፉ ናቸው።2. የዜጎች እና የህዝቦች ሰብዓዊና ዴሞክራሲያዊ መብቶች ይከበራሉ። ይላል። ይበል እንጂ ስልጣን ላይ ከወጣችሁ ቀን ጀምሮ በተግባር ያየነው የዚሁ ግልባጭ የሆነው የመብት ረገጣና ኣጃቢው ኣራዊታዊ ጭካኔ ብቻ ነው። ስለዚህም ሕገ መንግስት ኣስመልክቶ ኣንድ ቃልም ባይወጣችሁ ይመረጣል፣ ኣጉል መመጻደቅ ትርፉ ትዝብት ነውና።ሁለተኛው ምክንያታችሁ “ዕድገታችን የፈጠረው ችግር” ለወቅቱ ህዝባዊ ተቃውሞ መንሳኤ ሆነዋል የሚለው ደግሞ ጨቅላዊ(infantile) ስነ-ሞገት ነው። ዕድገት በመላ ዓለም እንደሚታወቀው ስራ ሲፈጥር፣ ብልጽግና ሲያመጣ፣ ድርቅና ችጋር ሲያጠፋ ነው። ከ 25 ዓመታት ኣገዛዛችሁ በሁዋላ በሃገራችን ሰፍኖ የሚታየው ደግሞ ስራ ኣጥነት፣ ድህነት፣ ድርቅና ችጋር ነው። የተባበሩት መንግስታት ዕድገት ፕሮግራም የኣምናው ሪፖርቱ (UNDP 2015 report HDI) እንደሚያሳየው 188 ሃገሮችን በ 4ክፍሎች (ሀ/ እጅግ ከፍትኛ፣ ለ/ ከፍትኛ፣ ሐ/ መካከለኛ፣ መ/ ዝቅተኛ) ብሎ ሲመድብ ኢትዮጵያን በዝቅተኛው ከማስቀመጡ ባሻገር ወደ 174 ኛ እርከን ዝቅ ኣድርገዋታል። በዚህ ላይ ድርቅን ተከትሎ የመጣው ችጋር ሰው-ሰራሽ ጥፋት መሆኑ ዓለም በተገነዘበበት በ 21 ኛው ክፍለ-ዘመን እናንት የምታቀርቡትዘገባ ጭራሽ ኣሳፋሪ ከመሆኑ በላይ ከሳይንሳዊ ጥናት ርቃችሁ እንደተኛችሁ ያመላክታል። 25 ዓመታት ስልጣን ላይ ተቀምጣችሁ፥ በኣሁኑ ዓመት ብቻ 10.2 ሚሊዮን ህዝብ በረሃብ እስኪሰቃይ ጠብቃችሁ ምጽዋት ልመና በየበሩ ስታንኩዋኩ ብዙ ሰው ታዘበ፣ እንደለመዳችሁት በረሃብተኛው ስም የሚመጣው ዕርዳታ ከፊሉ ህዝባዊ ተቃውሞን ለማፈን ፥ ከፊሉ ደግሞ ኣልጠግብ ባይ ኪሳችሁን ለማወፈር መሆኑ ከምትሰሩት ፎቅና ቪላ፥ ከምታስነዱት ደብዛዛ መስተዋቱ መኪና፥ በየባንኩ ከምታጭቁት ገንዘብ ኣልፎ ለስለላ ብቻ ከምታወጡት ወጪ ማወቁ ከባድ እንዳይመስላችሁ። በኣንጻሩ ገባሩ ህዝቡ ኣፈር ገፍቶ፥ ኣፈር መስሎ በምግብ ለስራ ተመጽዋች ሆኖ ኣሁንም በሰቅጣጭ ኑሮ መማቀቁ ልትደብቁት ኣትችሉም። “ገጠርን ማእከል ያደረገ ልማት” የምትሉትን ማዘናጊያ ፈሊጥ ውጤቱ ችጋር መሆኑ ለ 25 በተከታታይ መገንዘብ ተችለዋል። ያለፉት 16 ዓመታት የተባበሩት መንግስታት የዓለም ምግብ ፕሮግራም (WFP) እና የምግብና እርሻ ድርጅት (FAO) ሪፖርቶች መሰረት ያደረገ ጥናታዊ ጥንቅር እንደሚከተለው ያብራራል።
Year( ዓመት ) Starving Ple. Millions ( ረሓብተኛ በሚልዮን ) Source ( ምንጭ )
===================================================================================
2000 2.3 WFP
2002-2003 12.6 WFP
2004 7 FAO/WFP
2006 7.2 FAO
2008 10 FAO/WFP
2009-2010 5 FAO/WFP
2011-2012 13 WFP
2013-2014 +5 WFP
2015 10 WFP
2016 10.2 FAO/WFP
Table 1 – Mass starvation index 2000-2016 – Source: FAO and WFP
(ቅንብር የኔ)ታድያ በዓለም ከፍተኛ ከሚባሉት የ 11.5% ዕድገት ልፈፋችሁ ምንጩና ውጤቱ የት ላይ ነው? ምጽዋት ተግበስብሶ ኣዲስ የቱጃሮች መደብ ስለፈጠረ ዕድገት ሊሆን ኣይችልም። ዕድገት ባመዛኙ ችግር ቀራፊ እንጂ ችግር ፈጣሪ ኣይደለም። ዕድገት ባለመኖሩ ነው ችግር የተፈጠረውና ችጋር የሰፈነው። ስለዚህም ችግር የፈጠረው “ዕድገታችሁ’’ ሳይሆን የማይረባ ፖሊሲያችሁ፣ ኣፋኝ ኣስተዳደራችሁ፣ የስልጣን ስስታችሁ፣ ቅጥ ያጣ ሙስናችሁ ተደማምሮ ነው። በነዚህ 2 ምክንያቶች ብቻ ስልጣን መልቀቅ ነበረባችሁ። የህዝባዊው እምቢተኝነትና ተቃውሞ መነሻው ይኸው የናንተው የግፍ ኣገዛዝ ሆኖ እያለ፥ ኣንዴ በውጭ ሃይሎች፣ ሌላ ጊዜ በትምክህትና ጠባብነት ሃይሎች በማላከክ፣ ይባስ ብሎም የህዝቦች መተላለቅ እንዲከተል ትቀሰቅሳላችሁ። ኣባይ ‘የርዋንዳ እልቂት’፥ ስዩም ‘የኣይሁዶች ጭፍጨፋ-ሆሎከስትን’ በማውሳት ህዝቡቢያንስ በፍርሓት እንዲሸማቀቅ እየጣራችሁ ነው። ግን ህዝቡ ኣርቆ ስለሚያስብ እኩይ ጥረታችሁ ሊሳካ ኣልቻለም። ኣልቆበታልና። እንደሚታወቀው ማንም የውጭ ሃይል ለጥቅሙ ሲል ክፍተት ኣግኝቶ ይሁንና፥ ክፍተት ፈጥሮም እጅ ማስገባቱ እንዳለ ሆኖ፥ ታዲያ ክፍተት ፈጥሮ የውጭውን ጣልቃገብ የሳበ ኣካል በዋናነት ተጠያቂ መሆን ሲገባው ችግሩን በሌላ ማሳበብ ምን ይባላል? ይህ ክስተት የሞራልም የእውቀትም ደካማነት ያስከተለው ውስልትና ከመሆን ኣያልፍም።ትምክህትና ጠባብነት ደግሞ ድሮም የነበሩ ኣሁንም ያሉ ወደፊትም በድፍረት እስካልተዋጋናቸው ድረስ ሊኖሩ የሚችሉ የሕብረተሰብ ነቀርሳዎች ናቸው። በነዚህ ነቀርሳዎች የተነሳ ደህና የነበረው ሰውም እንዲለከፍና እንዲከፋፈል ቦዩን የቀየሳችሁ እናንተው፣ ሕጋዊ ልባስ ኣግኝተው ያንሰራሩትም በናንተው ዘመንነው። ከዚህ የተነሳ የሰከነ ውይይትና ጥናታዊ ዘገባ ተዳክሞ፥ ስነ-ሞገት ደብዝዞ፥ ኣጉል ንትርክና ቀረርቶ ጦፎ፥ ጽንፈኝነት እንዲስፋፋ ኣደረጋችሁ። በዚህ የጽንፈኝነት ወላፈን መከረኛው የትግራይ ህዝብ የጥቃቱ ዒላማ እንዲሆን ኣደረጋችሁ። የትግራይ ህዝብ ሰላምና ዕድገት ለኣያሌ ዘመናት ናፍቆ ኖሮ ህወሓት የመራውን ትግል ቢደግፍም ህልሙ እውን ሊሆን ኣልቻለም ብቻ ሳይሆን የባሰውን መከራ እንደወረደበት ኣርቆ ኣሳቢ የሆነ ሰው ሁሉ ሊረዳው የሚችል ሓቅ ነው። ስለዚህም በህወሓት ኣገዛዝ በችግርና በኣፈና የተወጠረ ህዝብ ህወሓትን የሚጠላበት እንጂ የሚደግፍበት ኣንድም ምክንያት የለውም። ከዴሞክራሲያዊና ሰብኣዊ መብቶቹ መገፈፍ ጀምሮ እስከ በድህነት ወጥመድ ተሸብቦ መኖር ያካተተ መከራ እየተጋተ ነው። እናንት በምቾት ጠምብሳችሁ፣ ጽንፈኞቹ ደግሞ በጥላቻ ተሸብበው የህዝቡን ኣሳዛኝ ሁኔታ መገንዘብ ኣልቻላችሁም። የኣብዛኛዎቹ ጽንፈኞች ችግር የታሪክ ድንቁርና፥ የጥላቻ ፖለቲካና የማገናዘብ እጥረት ወዘተ ያስከተለው ጣጣ ሲሆን በተለይ በህዝብና በኣምባገነን መንግስት መካከል ያለው ሰፊ ልዩነት በቅጡ ያለመረዳት ተቀዳሚው እጥረት / ጎዶሎነት ነው። እናንት “የትግራይ ህዝብና ህወሓት ኣንድ ኣካል ነው” እንደምትሉት ሁሉ ጽንፈኞችም ይህነኑ እንዳለ ይሉታል። ኣንዳንድ የሚዲያ ተቅዋማትም በሚያሳዝን ሁኔታ ይህንኑ ሲያራግቡ ይደመጣሉ። የጽንፈኞቹ ፍላጎት ህዝቡንም ደርቦ ለመምታት ሲሆን የናንተው ደግሞ በህዝቡ ጉያ ተወሽቆ ለመከላከል ነው። ሌላ ሚስጥር የለውም። የጥቂቶቹ ችግር ደግሞ ስግብግብነት ነው። ያው የናንተው ቅድ/ዓይነት መሆናቸው ነው። ጽንፈኞቹ ስልጣን ኣልያዙም እንጂ፥ ከቀናቸው እንደናንተው ስልጣኑና ሃብቱ ማግበስበስ ተቀዳሚ ሞያቸው እንደሚያደርጉ የሌሎች ሃገራት ጽንፈኞች እኩይ ታሪክ ያስገነዝበናል። የገብረመድህን ኣርኣያና የተክሌ ይሻው “በሬ ወለደ” ትረካ፥ ለዚሁ ዓይነተኛ ምሳሌ ነው። ‘ጅብ በቀደደው ውሻ ይገባል’ ተብሏል ኣይደል። የነዚህ ጽንፈኞች ሓላፊነት የጎደለው ትረካ – በዓለም-ኣቀፍ ሕግ ኣስጠያቂ የሆነው ኣደገኛ መዘዙ ሳንረሳ – ለጊዜው ኣቆይተን በኣንድ ልሂቅ ከተደረሰ ያልጠበቅኩት ጽሑፍ ላስነብባችሁ፦ ‘ ህወሓት ሲመሰረት ያዘጋጀው የመርህ ሰነድ የአማራን ብሄር ዋና ጠላት ማድረጉ የአደባባይ ምስጢር ነው።እንዲህ ይላል። “ የአማራ ሕዝብ የትግራይ ህዝብ ዋና ወይንም አውራ ጠላት ነው። ይኼ ብቻ አይደለም የአማራ ሕዝብ የትግራይ ሕዝብ ድርብ ጠላት ነው። ስለሆነም፤ እኛ ( ህወሓቶች ) የአማራውን ሕዝብ መምታት አለብን፤ መጨረስ አለብን። አማራው ካልወደመ፤ አማራው ካልተደበደበ፤ ከመሬት ካልተነቀለ፤ የትግራይ ሕዝብ በነጻነት ሊኖር አይችልም። እኛ የምንመሰርተው ተተኪ መንግሥት ጥንቃቄ ማድረግ ያለበት አማራው ዋና መሰናክል እንደሚሆንብን ነው”።’ (ሰረዝ የኔ)።እንደዚህ የሚል ሰነድ ኣልነበረም ፣ የለምም። ቀጥሎ በተሰራጨው ጽሑፋቸው ደግሞ ፦ህወሓቶች፤ በተለይ የህወሓት መስራቾች፤ “ዐማራውን አህያ” ከማለት ደረጃ የደረሱበት የራሳችን ድክመት፤ ዝምታ ማብዛትና በጥቃቅን ነገሮች ለመተባበር አለመቻል ጭምር ነው።’ ይላሉ።ይህም ስድብ በህወሓት መስራቾች ኣልተባለም። ኣይባልምም። ሁለቱ የፈጠራ ጥቅሶች ‘በህወሓቶች’ ያተኮሩ ቢመስሉም፥ 1 ኛ/ ከእውነት የራቁ ናቸው፥ 2 ኛ/ ህዝብ ከህዝብ ጋር የማጋጨት እንደምታ ኣላቸው። የኣማራ ገዢ መደብ እንደጠላት መቁጠር ግን እውነት የመርህ ሰነድ ሆኖ ይገኛል። ይህ ማለት ደግሞ የሁለቱም ጭቁን ህዝቦች የመደብ ኣጋርነት ድሮም የነበር፥ ኣሁንም ያለ፥ ወደፊትም የሚኖር፥ ከታሪካዊነቱ ኣልፎም መሰረታዊ የህዝቦች መደባዊ ኣሰላለፍን የሚያመለክት የመርህ ሰነድ መሆኑ ነው። በውነት! ህወሓትን የምንቃወምበት ተራራ የሚያክሉ ዓበይት ሃገራዊ ወንጀሎች የሌሉ ይመስል፥ በማስረጃ የማይደገፉ ኣልፎም ህዝብን የሚያቃቅሩ ክሶች ላይ መንጠልጠል ለምን ኣስፈለገ? ? ? የገብረመድህን ኣርኣያና የተክሌ ይሻው የጥላቻ ዘገባ እንደ ምንጭ የሚታሰብ ከሆነ ተያይዞ ገደል ውስጥ መግባት ነው። ይህ ዓይነቱ የዘውግ ፖለቲካ ዞሮ-ዞሮ ጉዳት እንጂ እርባና ስለሌለው ለጽንፈኞቹ ብቻ ቢተው፥ ዴሞክራቶችም በግልጽ ቢዋጉት ለሁላችን ይበጃል እላለሁ። ሌላ ኣሳዛኝ ብሎም ኣደገኛ መልእክት ደግሞ ከኢሳት በኩል በጋዜጠኛ መሳይ መኮንን ተደምጠዋል። በከፊል እንዲህ ይላል፥ “እኛን የገጠመን ትግል በማንኛውም ዓለም እንደሚከሰተው በጨቋኝ መንግስትና በተጨቋኝ ህዝብ ተብሎ በሚጠራው መካከል ሳይሆን በኣንድ ዘራችሁን በማጥፋት የበላይ ሆኜ ልግዛ በሚል ጎሳና ፍዳውኣላልቅ ባለው ሌላው የኢትዮጵያ ህዝብ መካከል ነው። . . . ይህ የጥፋት እቅድ የታቀደው ከ 5 ሚልዮን ህዝብ ለ 95 ሚልዮን ህዝብ ነው። . . . ወደድንም ጠላንም ምርጫው . . . የተበላሸን ዓሳ ከባህር ማስወገጃ መንገዱ ኣንድ ነው፥ የባህር ውሃ ማስወገድ” ii እያለ ይቀጥላል። መረን የለቀቀ ዘረኝነት ይሉታል ይህ ነው። በኣምባገነኖቹና ጌቶቻቸው ሴራ የታፈነው ታጋይ ኣንዳርጋቸው ጽጌ ‘ነጻነት የማያውቅ ነጻ ኣውጪ’ በሚለው ሃያሲ መጽሓፉ “. . . ብዙ የፖለቲካ ተንታኞች እንደሚሉት ወያኔ የያዘውን ስልጣን በመጠቀም ትግራይን ለመጥቀም በማሰብ ኣይደለም” (ገጽ.243)፣ “የወያኔ የጎሳ ፖለቲካ ፖሊሲ ከማንም ህዝብ፣ የትግራይን ህዝብም ጨምሮ፣ ደህንነት እና ጥቅም ጋር በቀጭን ክር እንኳን የተገናኘ ኣይደለም” (ገጽ244)፥ ሲል መሳይ የገባው ኣይመስልም። በዛ ላይ! ኤርትራ ድረስ በመዝለቅ የጎበኛቸው በሺዎች የሚቆጠሩየዴምህት (የትግራይ ህዝብ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ) ታጋዮች ከዚህ ግብታዊ ፍርድ ይተርፉ ይሆን? ይህ የዘር ማጥፋት ኣዋጅ በጋዜጠኛ መሳይ ተነበበ እንጂ ተደረሰ ለማለት ኣልደፍርም፣ ካንዴም ሁለቴ በቃለ-ምልልስ ጎን ተወያይተናልና። ያምሆኖ ግን የህወሓት/ኢህኣዴግ ጭፍጨፋዎች እንዳስመዘገብነው ሁሉ ይህን ዘግናኝ ጸረ-ህዝብ ኣዋጅም ወደሚመለከተው ዓለም-ኣቀፍ ተቋም ማስተላለፋችን ይታወቅልን። የመደብ ኣሰላለፍ ስነሓሳብን ያውቃሉ የሚባሉ ኣባላት ያሉበት ኢሳት ወደዚህ መውረዱ ኣሳዛኝም ኣስኮናኝም ነው። ‘ብሄሬ በኢትዮጵያዊነት እሳት ቀልጧል’ ያልው፥ ከጥላቻ ፖለቲካ የጸዳ፥ የምር ኢትዮጵያዊው የፍትሕ ታጋይ ተክለሚካኤል ኣበበ “የኛ ነገር፤ ትግሬን መነጠል፤ ሐሳዊ-ኢትዮጵያዊነት ነው”iii በሚል ርእስሰሞኑን የደረሰውን ኣርቆ-ኣመላካች ጽሑፍ ውስጥ ”የአማራ ህዝብ በስሙ ግፍ ከተሰራ፤ ግፍ ሰሪዎቹ እንጂ አማራው እንደማይጠየቀው ሁሉ፤ የትግራይ ህዝብም እንደዚያ በስሙ ለሚሰራ ግፍ ተጠያቂ ሊሆን አይችልም . . . ትግሬን ብቻ ነጥሎ የሚከስ አካሄድ፤ ጸረ-ኢትዮጵያዊ ነው ” ይላል—— እነዚህ ዓይነቶቹ ገንቢ ስነ-ጽሑፎች ብናነባቸውስ! (ሊንኩ ታች ኣለ)፣ ወይም ደግሞ ያለ ኣንድ ምክንያት 4 ዓመታት ከ 8 ወራት በግፍ ታስረው የተሰቃዩት የኢትዮጵያ ሙስሉሞች መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ ኣባላት መስከረም 1/2009 ዓ/ም ያካፈሉንንበሳል መልእክት ብናጤነውስ፣ ከገንቢ መግለጫቸው በከፊል፦“ከየትኛውም ወገን የሚሰነዘሩ፣ ህዝብን ከህዝብ ሊያጋጩ የሚችሉ፣ አንዱን የተለየ ብሄር ወይም ማህበረሰብ አጠቃላይ በሆነ መልኩ የሚያወግዙ፣ የሚያስገልሉና በእኩይነት የሚፈርጁ የጥላቻ ፕሮፓጋንዳዎች አገርን አደጋ ላይ የሚጥሉ በመሆናቸው ይህን መሰል ሁኔታ እንዳይፈጠር ከፍተኛጥንቃቄ ሊደረግ ይገባል—— የተለያዩ ባለድርሻ አካላትም ጸረ-ህዝብ እና አፍራሽ አካሄዶች እንዳይፈጠሩየመከላከል ስራቸውን ከመስራት እንዲይዘናጉ አጥብቀን እናሳስባለን” ይላል። የህዝቦች ኣጋርነት ማጎልበት፥ የጽንፈኞች ሴራ ማክሸፍ፥ በጥቅሉ ኣርቆ-ኣሳቢነት ይሉታል በእንዲህ ያለ መርህ መቆም ነው። የሁለት ስለት ሰለባ የሆነው የትግራይ ህዝብ ምን ዓይነት ኣጣብቂኝ ውስጥ እንደሚገኝ ማገናዘቡና ኢትዮጵያዊ ኣጋርነቱን እንደጥንቱ እንዲያጎለብት መተባበሩ ለምናካሂደው ስትራቴጃዊ የጋራ ትግል እጅግ ጠቃሚ በመሆኑ የፍትሕ ወገን የሆነ ሁሉ የ“ድምጻችን ይሰማ” መርህ በኣጽናኦት ማስተጋባቱ ኣስፈላጊ ነው እላለሁ። እነዚህ ዓይነቱ ኣመለካከቶች የኢትዮጵያ መጪው ብሩህ ጊዜ መንገድ ቀያሾች ስለሆኑ በትጋት ልናስተጋባቸውም ይገባል። እግረ-መንገዴ ያነሳሁት ኣሳሳቢ ጉዳይ እዚህ ላይ ልገድበውና ወደናንተ ወደ ቱጃሮቹ ልመለስ። የዛ ሁሉ የጥላቻ ፖለቲካ ሰበብ እናንተው የወቅቱ ባለስልጣኖቹ፥ ሕጋዊ ሽፋን በመስጠት ያራመዳችሁት የዘውግ ፖለቲካ መሆኑ ደጋግሜ ላሰምርበት እፈልጋለሁ፣ በኣጽናኦት። ኣሁን በሃገራችን ላንሰራራው ኣጠቃላይ ዝቅጠት ዋናው ተጠያቂ፣ ራሳችሁ በትክክል እንደገመገማችሁት የናንተው “የበሰበሰ ኣመራር” ሆኖ እያለ በናንተ ኣሰራር ምክንያት ሁሌም ገፈት ቀማሹ፣ መከራ ተሸካሚውና ኣፈናው ኣላላውስ ያለው የትግራይ ህዝብ ኣብሮ ተወቃሽ የሚያደርጉ ድምጾች መሰማታቸው የባሰውኑ ልብን የሚያቆስል ነው። የደርግ ኣመራርን ከሰራዊቱና ከህዝቡ ጋር ደምሮ መምታት እንደማለትም ነው። ስር የሰደደው የናንተው (የህወሓት/ኢህኣዴግ) ክፉ ኣገዛዝ እንዳይበቃው፣ ኣፋኙና ታፋኙ፥ ድሃውና ቱጃሩ፥ ገዢውና ተገዢው የማይለይ ውርጅብኝ በህዝቡ ላይ ማወረድ ለምንስ ኣስፈለገ? ከላይ በናንተው ጨካኝ ኣፈና፣ ከታች ደግሞ ህዝቡን ከሌላው ኢትዮጵያዊ ወገኑ የሚነጥል ጉንተላ፣ ውስጥ ተወጥሮ ያለው ህዝብ ኣንድነቱን ኣሳምሮ ሲነሳ ቀን ግን ግብኣተ-መሬታችሁ መሆኑ እወቁት። ይህ ደግሞ ሩቅ ኣይደለም።በርግጥ ኣይቀሬ ውድቀታችሁ ከጀመረ ውሎ ኣድሮዋል። እየተቀላጠፈም ነው። ምናልባት ከሙስና ጫካ ውስጥ መሽጋችሁ የከበብዋችሁን ተራሮች ላይታይዋችሁ፥ የተቀጣጠለው የእምቢተኝነት ድምጽ ላይሰማችሁ ይችላል። ቀደም ሲል “ድምጻችን ይሰማ” በሚል መርህ የተነሳው የሙስሊም ወገናችን እንቅስቃሴ፣ ቀጥሎ በኦሮሞው፥ በኣማራው፥ በሲዳማው፥ በጋምቤላው፥ በኣፋሩ፥ በኦጋዴኑ . . . .ወዘተ ትግሉ ተፋፍመዋል። በትግራይም እንዲሁ ለጊዜው ያዳፈናችሁት የተምቤን ዓቢይ-ዓዲ፥ የኣጽቢ፥ የነበለት፥ የመቀሌው ፍትሕ ፍለጋ እምቢተኝነት ተጠናክሮ ዳግም ይነሳ ዘንድ እየተፋፋመ ነው። ስዩም “ከገባንበት ኣዘቅት በፍጥነት መውጣት ኣለብን፣ . . . ኣለዚያ ኣወዳደቃችን ኣያምርም” ስትል ስለ ኣወዳደቁዓይነት (ማማር ወይም ኣለማማር) ብቻ ሳይሆን ውድቀቱም የጀመረ ለመሆኑ የገባህ ይመስላል። እንግዲህ የኣወዳደቁ ምርጫ ለናንተ የሚተው ሆኖ፣ ያሉትን ኣማራጮ ከሚታገልዋችሁ የፖለቲካ ሃይሎች ኣንጻር ልጠቁም ፣ ከትግራይ ብጀምር 1. ዓረና ትግራይ በሰላማዊ ምርጫ፥ 2. ዴምህት በትጥቅ ትግል፥ 3. ትዴት/ታንድ በህዝባዊ ኣመጽ፥ የሚሉ ሆነው እነዚህ ሶስት ኣማራጮች በሃገር ደረጃም ተጠቃለው የሚቀርቡ ናቸው፣ ማለትም ዓረና በመድረክ፥ ዴምህት በኣርበኞች ግ/7፥ ትዴት በሸንጎ ተደራጅተው ይቀርባሉ። ከፖለቲካ ሃይሎች ውጭ ደግሞ ኣያሌ ግለሰቦችና የሲቪክ ንቅናቄዎች የየበኩላቸው ኣማራጮች እያቀረቡ ይገኛሉ። በስደት ከሚኖሩ የትግራይ ተወላጆች ሽዎችን የሚወክሉ 34 ቱ ‘‘ውረዱና የሽግግር መንግስት ይቋቋምበት’’ የሚል የማያወላዳ መፍትሄ ሰንዝረዋል። ተጠቃሎ ሲታይ ኣማራጮቹ ከጥገናዊ ለውጥ ጀምሮ እስከ ስር-ነቀል ለውጥ ያካተቱ ቢሆንም ዞሮዞሮ የናንተው ኣምባገነናዊ ስርዓት ተወግዶ በህዝባዊ-ዴሞክራሲያዊ ስርዓት መተካት እንዳለበት መደምደሚያው ነው። ስለሆነም የኣወዳደቅ ዓይነቱ ምርጫ ለናንት ለቱጃሮቹ እየተውኩ፥ የሁኔታው ኣጣዳፊ ነት ግንተጨባጭ መሆኑ ከሰማችሁኝ ላስገነዝባችህ እወዳለሁ። ዘመኑ ደንቆሮም የሚሰማበት ጊዜ ነውና!
(በምልክትቋንቋ/sign language):: በእውነት ጊዜው ደርሰዋል፣ ያንድ ትውልድ ዘመን ስልጣን ላይ ተቀምጣችሁ፥ ሰለሞን ነጋሽ “የትግራይ ህዝብና የህወሓት ግኑኝነት ነባራዊ ገጽታ”iv በሚል ርእስ በጥልቀት እንደተነተነው 80% የትግራይ ህዝብን የምግብ ለስራ/ሴፊቲ-ኔት ተመጽዋች በማድረግ ለመናጢ ድህነት ዳርጋችሁ፣ መላው የኢትዮጵያ ህዝብም በዚሁ ሁኔታ እንዲኖር እያስገደዳችሁ፥ እናንት የናጠጡ ቱጃሮች ሆናችሁ ስልጣን ላይ እንቆያለን ማለት ከዕብደት ያልራቀ ቅዠት ነው። ኣፈናም ሆነ ሙስና፥ ክልል-ዘር-ሃይማኖት የለውምና ጠቅላላ የኢትዮጵያ ህዝብ የ 25 ዓመታት የኣፈናና የግድያ የድህነት ኣገዛዝ በቃኝ! በቃኝ! በቃኝ! “ፍርሓት ኣለቀብኝ” ብሎ ከጫፍጫፍ ተነስቶባችሁ ይገኛል። የመላ ኢትዮጵያዊ ግንዛቤ የሚወክል በወንድም ሠማነህ ርቱዕ ኣንደበት ከተላከልን ሰፊ ሓትታ ቀንጭቤ ላካፍላችሁ፣ “በስልጣን ላይ ያሉት ሰዎች አሁን የሚታያቸው የሃገራቸው፣ የኢትዮጵያዊያን፤የትግራይ ክፍለሃገርና የትግራይ ሕዝብ ሁኔታ ሳይሆን ንብረታቸው፤ ጥቅማቸውና ስልጣናቸው ብቻ ነው። . . . ” ይላል። ደረቅ ሓቅ ኣይደል! ስልጣን ላይ ደግሞ ለዘለዓለም ኣይኖርም። ሃገሮች የ 4፥ የ 5 ወይም የ 8 ዓመታት የስልጣን ገደብ የሚደነግጉት ያለምክንያት እንዳልሆነ ይግባችሁ። ሰሞኑን በጎንደር ኣሁን ደግሞ በብሸፍቱ ወገኖቻችን ላይ ያካሄዳችሁት ኣሰቃቂ ጭፍጨፋ ኣራዊታዊ ባህሪያችሁ የሚያጋልጥ ተጨማሪ የውድቀታችሁ ምልክት ነውና ይብቃችሁ። እንደ ህዝቡ እናንተም በቃን በሉ። ሁሉም የፖለቲካ እስረኞች ፍቱ። ከያቅጣጫው የሚዘንበው የመፍትሄ ጥሪ ኣዳምጡና ተግብሩ። ኣለዚያ ብርሌው ነቅቷልና መንኮታኮት የግድ ይላል።የትግራይ ህዝብ በኣምባገነኖች ኣይገዛም!!!የህዝቦች ኣንድነት ይለምልም!!!የትግራይ ኢትዮጵያዊነት በመሰሪዎች ኣይናድም!!!ኢትዮጵያ በሩቅ-ኣሳቢ ልጆችዋ ህብረት ትነሳለች!!!


በህዝባዊ ተቋውሞ የተወጠረው ወያኔ በጀርመኑዋ ካንስለር አንጌላ ሜርክል ጫና ሊገጥመው ነው ።

0
0

ለተጠናከረው ዘገባ ዘርይሁን ሹመቴ ከጀርመን
http://www.addis-abeba.diplo.de/
የጀርመኑዋ መርሃ መንግስት አንጌላ መርክል (Chancellor Dr. Angela Merkel) በ 11/10/ 2016 እኤአ ( 30/ 01/ 2009 ዓም) ይፋዊ የሰራ ጉብኝት በኢትዮጵያ እንደሚያደርጉ ታወቀ። የወያኔ መንግስት በአገር ውስጥ በከፍተኛ የህዝብ ተቋውሞና አልገዛም ባይነት ተወጥሮ ባለበት ባአሁኑ ወቅት እንደዚህ ያለው ጉብኝት ከወዳጆቹ ምእራባውያን ለተጨማሪ ነቀፌታ እንዲሁም ጠጠር ላለ ጫና ሊዳርገው ይችላል። በቢሾፍቱ የኢረቻ በአልን ለማክበር በወጡት ኢትዮጵያውያን ላይ የወያኔ መንግስት በተጠቀመው የአስለቃሽ ጢስ ጥይት ምክንያት ህይወታቸው ያለፈው ወደ 680 በደረሰበት ፣ በመላው የአማራ ተወላጅ ላይ ግልጽ የሆነ ጦርነት በታወጀበት ፣ በአፍሪቃ መቀመጫና የተለያዩ አገራት ኤምባሲ በሚገኝባት በአዲስ አባባ የኢንተርኔትና የማህበራዊ ሚዲያዎች በተዘጉበት በዚህ ጊዜ ወያኔ እንኩዋን በቀጠናው በኢትዮጵያ ውስጥ ሰላም ማስፈን እንደተሳነው እንዴት አድርጎ ለጀርመኑዋ ካንስለር አንጌላ መርክል ማስረዳት እንደሚችል ትልቅ የቤት ስራና የራስ ምታት ሆኖበታል። በአዲስ አበባ የጀርመን ኤምባሲ ባወጣው ጋዜጣዊ መግለጫ መሰረት የአንጌላ መርክል የስራ ጉብኝታቸው ዋናው ምክንያት በቀድሞ የታንዛኒያ መሪ በነበሩት ጁሊዬስ ኔሬሬ (Julius Nyerere) ስም የተሰየመውን አዲሱን የሰላምና ደህነት ህንጻ ለማስመረቅ እንደሆነ መረዳት ተችሏል። ካንስለር ሜርክል በዚሁ ህንጻ ንግግር እንደሚያደርጉም መግለጫው ጠቅሱዋል። ይህ ህንጻ በጀርመን መንግስት የገንዘብ እርዳታ እንዲሁም የጀርመን ተቋራጭ የተገነባ መሆኑን ኤምባሲው በመግለጫው አስፍሯል። የመላ ኢትዮጵያውያንን ሰላምና ደህንነት እየነፈገ አምባገነኑ የወያኔ መንግስት በቀጠናው ሰላምን አሰፍናለሁ በሚል ሰበብ የስልጣን እድሜውን ለአንድም ቀን ብትሆን ለማራዘም ለምእራብያውያን ጉዳይ አስፈጻሚና ሎሌ ከሆነ ሁለት አስርተ አመታት አልፈውታል። በርግጥም የወያኔ መንግስት ለውስጥ (ለህዝቡ) ቀካ ለውጭ አልጋ ነው። የጀርመን መንግስት በከፍተኛ ገንዘብ ይህንን ህንጻ ያሰራው ገና ለገና ወያኔ ደሃውን የኢትዮጵያ ሰራዊትን( የተደላደሉትን የአጋዚ ወታደሮችን አያካትትም ) በሱማሌ ይገብርልናል በሚል እሳቤ እንጂ እውነተኛ ሰላምን ደህንነትን እንዲሁም ዲሞክራሲን አስቦ እንዳልሆነ መረዳት ይቻላል። ለዚህም ማስረጃ በወያኔ መንግስት ትእዛዝ የአጋዚ ወታደሮች በኦርምያ፣ በጎንደር፣ በባህር ዳር፣ በጎጃም፣ በኮንሶ፣ በጋምቤላ እንዲሁም በተለያዩ የኢትዮጵያ ክፍሎች በሰላማዊ ሰልፈኞች ላይ ያደረሱትን አረመናዊ የሆነ ግድያ መመልከት በቂ ነው። ወያኔ የበግ ለምድ ለብሶ ተኩላ መሆኑን( እንኩዋን አሽባሪን ሊዋጋ እራሱ አሽባሪ መሆኑን) በሰላማዊ መንገድ ተቋውሟቸውን ለመግለጽ አደባባይ በወጡ ንጹሃን ዜጎች ላይ እየወሰደ ባለው ግድያ፣ አፈና፣ እስራትና ድብደባ በተግባር ለአለም አረጋግጧል።
angela
ምእራብያውያኑ አፍሪቃን የመቀራመት አባዚያቸው በአሃጉሪቷ ውስጥ በከፍተኛ ተቀባይነት እንቅስቃሴ በምታደርገው ቻይና ምክንያት እንደገና እያገረሸባቸው ይገኛል። 200 ሚሊዮን
ዶላር በማውጣት የቻይና መንግስት በ 2012 እኤአ የአፍሪቃ ህብረት ህንጻን በስጦታ መስጠቱ ምእራባውያንም አትኩሮታቸውን ወደ አፍሪቃ እንዲያደርጉ አስገድዷቸዋል። ለዚህም ይመስላል የጀርመን መንግስት ይህን በጁሊዬስ ኔሬሬ ስም የተሰየመውን አዲሱን የሰላምና ደህነት ህንጻ ፈንድ በማድረግ ያሰራው። ከጸጥታና ደህንነት በተጨማሪ የካንስለር አንጌላ መርክል የኢትዮጵያ ጉብኝት የስደተኛ ጉዳይን ይጨምራል ተብሎ ይገመታል። በ 11/ 10/ 2016 የጀርመን ኤምባሲ ከአለም የምግብ ፕሮግርም(WFP) ጋር በመሆን ባወጣው ጥምር ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ በኢትዮጵያ የጀርመን አምባሳደር የሆኑት ዮሃም ሽሚትስ (JoachimSchmidt) የስደተኛ ጉዳይ በጀርመን ውስጥ አንገብጋቢ የፖለቲካ ጥያቄ መሆኑን ገልጸዋል(http://www.wfp.org/news/news-release/germany-provides-more-critical-support-refugee-food-assistance-ethiopia) ። የወያኔ መንግስት ቁንጮ የሆኑት አቶ ሃይለማሪያም ደሳለኝ በኢትዮጵያ በአየር መዛባት ወይም ኤል- ኒኖ መንስኤ ተከስቶ በነበረው የረሃብ ችግር በኢትዮጵያ ውስጥ ተጠልለዋል ያሉትን የደቡብ ሱዳን፣የኤርትራንና የሶማሌን ስደተኞችን እንደ ምክንያት ማቅረባቸው ይታወሳል(http://www.aljazeera.com/news/2016/03/ethiopia-calls-international-drought-bites-160317142601295.html ) ። እነዚህ ስደተኞች ወደ አወሮፓ እንዳይመጡ ለመከላከል ምእራባውያኑ ለወያኔ ዳጎስ ያለ ገንዘብ በየአመቱ እንደሚለግሱት ቢታወቅም በቅርቡ የአውሮፓ ህብረት የወያኔ መንግስት በኢትዮጵያውያን ላይ በሚያደርገው የመብት ጥሰትና ግድያ ምክንያት ያቀደውን የገንዘብ እርዳታ ላልተወሰነ ጊዜ እንዲቋረጥ በ 06/ 09/ 2016 እኤአ መወሰኑ ይታወሳል(https://www.euractiv.com/section/development-policy/news/weds-no-emergency-trust-fund-money-goes-to-ethiopian-government-commission-stresses/ ) ።የጀርመን መንግስት እነዚህ ስደተኞች በኢትዮጵያ ውስጥ እንዲቆዩ ከ 4 ሚሊዮን ዶላር በላይ በ 2016 እኤአ ለግሷል። ይህን የካንስለር አንጌላ መርክልን የኢትዮጵያ ጉብኝትን በመቃወም በጀርመን የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን የተቋውሞ ሰልፍና የፔትሽን ፊርማ ማሰባሰብ ፕሮግራሞችን አድርገዋል።sources http://www.addis-abeba.diplo.de/https://www.euractiv.com/section/development-policy/news/weds-no-emergency-trust-fund-money-goes-to-ethiopian-government-commission-stresses/ http://www.aljazeera.com/news/2016/03/ethiopia-calls-international-drought-bites-160317142601295.html http://www.wfp.org/news/news-release/germany-provides-more-critical-support-refugee-food-assistance-ethiopiaBy Zerihun Shumete/ from Germany

የኃዘን መግለጫ –ከቀድሞ የኢትዮጵያ አየር ኃይል ማህበር በዋሽንግተን ዲሲ ኦክቶበር 8, 2016

0
0

የኃዘን መግለጫ
ከቀድሞ የኢትዮጵያ አየር ኃይል ማህበር በዋሽንግተን ዲሲ ኦክቶበር 8, 2016

airforce-ethiopia
መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ፤ እንዲሁም የኢትዮጳያ አየር ኃይል ፤ ዛሬ ዕውቅ ጀግና ልጁን አጥቷል። ብ/ጄኔራል ለገሠ ተፈራ የዘላዓለም ዕንቅልፍ አንቀላፍቷል። ስለ እርሱ አለቀ ደቀቀ ማለታችን አይደለም፤ እንደውም በድፍረት አልሞተም እንላለን። የሀዘን እንጉርጉሮ አንደረድርም፤ ደረትም አንደቃም። ይልቅስ የሀገራችንን ነፃነትና ሉአላዊነት ለመጠበቅ ያከናወናቸውን ድንቅ የአየር ላይ ውጊያዎቹን እያስታወስን እንዘምርለታለን። በሃገራችን ታሪክ ውስጥ ስሙ ህያው ሆኖ ይኖራል። ሞቱ አይታየንም፤ የሚታየንስ የጦር ሜዳ ውሎው ነው። የከፈለውን መስዋዕትነት ስናስብ እንደነቃለን፤ እንገረማለንም። ዛሬ ለጀግናው ብ/ጄኔራል ለገሠ ተፈራ የሚገባው ጭብጨባ ነው።

በ 2008 ዓ.ም እ.ኤ.አ “የቀድሞው አየር ኃይል ማህበር በዲሲ” ብ/ጄኔራል ለገሠ በዋሽንግተን አካባቢ እንደሚኖርና በጤናው በኩል ችግር እንዳለበት ጥቆማ ይደርሰዋል። ማህበሩም በአስቸኳይ ኮሚቴ አቋቁሞ ምን መደረግ እንዳለበት ከተወያየ በኋላ፤ አብዛኛዎቻችሁ እንደምታስታውሱት “የጀግና ምሽት” በማዘጋጀት፤ ብ/ጄኔራል ለገሠንና መላውን ቤተሰቦቹን በመጋበዝ የተለያዩ ሽልማቶችን በመሸለም ጄኔራሉ የሀገራችንን ዳር ድንበር ለማስከበር ያደረገውን አስተዋፅዖ በተለያየ መልኩ እንዲዘከር አድርጓል። በግዜው የተለያዩ የቴሌቪዥን ጣቢያዎችና የኤፍ ኤም ሬዲዮ ጣቢያዎች ስለ ጀግናው አባላችን ሲያስተዋውቁትና ሲያወድሱት ከርመዋል። ማህበሩ የፈፀመው ተግባር እሰየው የሚያስብል ነበር። የቀድሞው አየር ኃይል ማህበር ከሌሎች ሀገር ወዳድ ኢትዮጵያውያን ጋር ይህንን ሳያደርግ ቀርቶ ቢሆን ኖሮ ዛሬ ምንኛ ይፀፅተን ነበር?

ዛሬ የብ/ጄኔራል ለገሠን የጦር ሜዳ ውሎ ብንዘክር ደስ ባለን..ነበር፤ ነገር ግን ከግዜ አንፃር ሲወሰድ ምቹ ስለማይሆን ልናልፈው ተገደናል። ከዚህ በፊት ባሳተምናቸው መፅሄቶች አውስተናቸዋል። ለገሠ ሞትን ፈርቶት አያውቅም። ሁልግዜ ከጎኑ እንዳለ ጓዳኛ ነበር የሚቆጥረው። እንደውም በዛ ቀውጢ ጦርነት ሞትን አሸንፎት ነበር ብንል ስህተት አይሆንም.. ተወልዶ መሞት ያለ ጉዳይ ነው። ለገሠ ቢሞትም ሥራውና ስሙ ከመቃብር በላይ ነው። ለመላው ቤተሰቡ፣ ለዘመዶቹ፤ ለቀድሞ ሥራ ባልደረቦቹ፤ ለጓደኞቹ መፅናናትን እየተመኘን ይህን የመሰለ ኣጋራችንና መኩሪያችንን በማጣታችን ቅር ብንሰኝም፤ ጀግንነቱን ስናስታውስ ልባችን ይፅናናል።

ለገሠ በአካል ብትለየንም በልባችን ውስጥ ግን ለዘለዓለም ትኖራለህ !
www.formerethiopianairforce.org (amfea_dc@yahoo.com)

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን የማን ናት? [ ክፍል ፩]

0
0

በአቻሜለህ ታምሩ

ብዙ ሰው ኢህአዴግ በሚባለው የማታለያ ጭምብል ውስጥ ስላለው የወያኔ የበላይነት እያወራ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ያለውን የትግራይ የበላይነት ግን የዘነጋነው ይመስለኛል። «አቡነ» ማቲያስ የሚባሉት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ፓትሪያርክ በዜግነት አሜሪካዊ ናቸው። ለወትሮው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ከርስቲያን ፓትሪያርኮች ከግብጽ አሌክሳንደሪያ ይሾሙ ነበር። ኢትዮጵያ ከአሜሪካ ጳጳስ አስመጥታ ፓትሪያርክ ስታደርግ ግን ማቲያስ የመጀመሪያው ናቸው።
ማቲያስ ሱዳን ሳሉ የመንገሻ ስዩም ቃል አቀባይና የኢዲዩ የፕሮፓጋንዳ ጋዜጠኛ ነበሩ። አሜሪካ ገብተው ማተባቸውን ቆርጠው አሜሪካዊነትን ከተቀበሉ በኋላ በሀገረ ኢየሩሳሌም የታሪካዊቷ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን «ሊቀ ጳጳስ» ሆነው ተሹመው «አጎታቸውን» ፓትሪያርክ ጳውሎስን እስከተኩበት ጊዜ ድረስ በነበራቸው የኢየሩሳሌም ቆይታቸው ሙስናን ተቋማዊ አድርገውት ነበር። አንዳንድ ሰዎች «በብዝሀነት» ሲመዘን «እየሩሳሌም ካለው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን አስተዳደር መቀሌ ያለው የአቡነ አረጋዊ ደብር ይሻላል፤ ቢያንስ የተወሰኑ የኢሮብ ሰዎች አሉበት» ሲሉ ሰምቻለሁ።
የማቲያስ ጉድ ተነግሮ አያልቅም። ወያኔ ሻዕብያን ተከትሎ አዲስ አበባን በተቆጣጠረ ማግስት ሎስ አንጀለስ የሚገኘውን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ለሁለት ከፍለው የትግራይና የኢትዮጵያ በሚባሉ ሁለት ቤተ ክርስቲያኖች እንዲፈጠሩ ያደረጉ የዛሬው የወያኔ ፓትሪያርክ «አቡነ» ማቲያስ ናቸው።
ማቲያስ በኢትዮጵያ ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ መንግስት ነኝ ባዩ ነውረኛ ቡድን ያዘጋጀውን ድግስ ለመታደም የአመቱን የቁልቢ ገብርኤል ንግስ ሳያከብሩ የቀሩ ብቸኛ «ፓትሪያርክ» ናቸው። የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻቸው የሆኑት ተራ ምዕመናን ከሩቅ ቦታ ሳይቀር በመጓዝ የአመቱን ገብሬል ለማክበር ወደ ቁልቢ ሲተሙ እሳቸው ግን «ብርሀን ከጨለማ ጋር ህብረት የለውምና ተለይ» የሚለውን «አባታዊ» ቡራኬ እና ቃለ ምዕዳን ተገኝተው ለምዕመኑ ይሰጣሉ ተብሎ ሲጠበቅ «አመንዝረው» በገብርዔል ፈንታ ከአቦይ ስር ሸራተን ዋሉ። በመንፈሳዊነት የከሰረች አገር!
እኒህ ቤተ ክርስቲያኗን በመንፈሳዊነት ያከሰሯት ሙሰኛ «አቡን»፤ የኢትዮጵያን ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያንን ቤተ ትግሬ አድርገዋታል። ይህንን በሚመለከት «ብጹእነታቸው» በሀይማኖት ካባ የሰሩትንና እየሰሩ ያሉትን ወንጀል፣ ሙስናና ዘረኝነት በማስረጃ በማስደገፍ በተከታታይ እናቀርባለን።
ለዛሬው የማቀርበው ማስረጃ ባለፈው ጊዜ የአዲስ አበባን ሀገረ ስብከት በጠራራ ጸሀይ ዘርፈው እንዲነሱ የተወሰነባቸውን ሶስት የትግራይ ሌቦች በነማን እንደተኳቸው የሚያሳይ ዶሴ ነው። «አቡነ» ማቲያስ በተለይ ጠርቀም ያለ አስራት በኩራት የሚሰበሰብበትን የአዲስ አበባን ሀገረ ስብከት የበላውና የጠገበው ዘመዳቸው ሄዶ የራበውና ሁሉ ብርቁ የሆነ ዘመዳቸው የሚተካበት የትግራይ ርስት አድርገውታል። ብጹዕነታቸው የቀድሞዎቹን የበሉና የጠገቡ ሶስት «ሀጎሶችን» ወደሌላ አዛውረው በነሱ ቦታ የተኳቸው አዲሶቹ የአዲስ አበባን ሀገረ ስብከት ገዳማትና አድባራት ሹመኞች የሆኑት ሶስቱ የራባቸውና ሁሉ ብርቁ «ሀጎሶች» እነሆ!

14560063_1247570698598210_8279325083815689279_o

አልሸሹም ዞር አሉ እንዳይሆን –ሰማሀኝ ጋሹ (ዶ/ር)

0
0

 

Et_olf1.pngየኦሮሞ ቻርተርና ወታደራዊ ክንፍ መቋቋምን በተመለከተ የሚመክር በአትላንታ የሚካሄድ ስብሰባ ዜና እና ሰነድ ይፋ ከተደረገ በሗላ በተለያዩ ወገኖች ዘንድ ጥርጣሬና ጥያቄ አስነስቷል። ጋዜጠኛ ሳዲቅ አህመድ አቶ ጃዋርንና ፕ/ር ህዝቄልን የኦሮሞ  ቻርተርን በተመለከተ ውይይትም አካሂዷል። በውይይቱ ወቅት የመገንጠል ጥያቄዉን በተመለከተ ጥሩ ማብራርያ የተሰጠ ቢሆንም አሁንም በርካታ መልስ የሚሹ ጉዳዮች አሉ። በተለይ አትላንታ ይካሄዳል ተብሎ የታሰበዉን ስብሰባ በተመለከተ የወጣዉ መግለጫ በብዙዎች ዘንድ ያልተጠበቀ ነገር ነዉ። በጎንደር በተካሄዳዉ የተቃዉሞ ሰልፍ ወቅት ህዝቡ ‘ የኦሮሞ ደም የኛ ደም ነዉ’  ፥ ‘ በቀለ ገርባ መሪያችን ነዉ’ በማለት ለኦሮሞ ህዝብ የተቃዉሞ እንቅስቃሴ ያለዉን አጋርነት ከገለፀ በሗላ በህዝቦች መካከል የነበረዉንና በህወሓት ለዘመናት የሚዘወረዉን የከፈፍልህ ግዛ  (divide and conquer)  ፖለቲካ በማዳከም ከፍተኛ የትግል አንድነት ያመጣ መሆኑ ይታወቃል። ህዝቡ ይህንን የተፈጠረዉን አንድነት የሚያጠናክር የፖለቲካ ሀይሎች የጋራ መድርክ ሲጠብቅ የተናጥል ስብሰባ መጠራቱ በብዙዎች ዘንድ ጥርጣሬ መጫሩ የሚጠበቅ ነዉ። ከዚህ አኳያ የተፈጠረዉን የህዝብ አንድነት ሊያጠናክር የሚችል ስራ ላይ ማተኮር ሲገባ የተናጠል የስብሰባ ጥሪ መጠራቱ  በጋራ ትግሉ ላይ የራሱን ተፅእኖ ማሳደሩ የማይቀር ነዉ።

 

ከዚህ የከፋዉ ደግሞ የቀረበዉ ሰነድ ስለ ህዝቡ የጋራ ትግልና የደረሰበትን ደረጃ  ጨርሶ አያነሳም።  ሰነዱ ወደፊት የኦሮሞ ህዝብ በኢትዮጵያ የፖለቲካ ስርአት ዉስጥ የሚኖረዉን ሚና በተመለከተም ምንም አይነት ፍንጭ ያልሰጠ ሲሆን   የኦሮሞን ህዝብ በደሴትነት ተነጥሎ የተቀመጠ ያስመስለዋል። እንደዉም ሰነዱ የኦሮሞ ህዝብ ከኢትዮጵያ ጋር ያለዉን ግንኙነት የቅኝ ግዛት አድርጎ ያቀርበዋል። የቅኝ ግዛት ትንታኔዉን (colonial thesis) በርካታ የኦሮሞ ምሁራንና ፖለቲከኞች እንደማይደግፉት እየታወቀ ሁሉንም የኦሮሞ መሪዎች ላማሰባሰብ ያለመ ሰነድ ለምን ያአንድ ወገን አቋም ብቻ ለማንፀባርቅ እንደፈለገ ግልፅ አይደለም። የኦሮሞ ህዝብ ከኢትዮጵያ ህዝብ ጋር ያለዉን ግንኙነት የቅኝ ግዛት ጥያቅ እንዳልሆነ የሚያምኑትን የኦሮሞ ፖለትከኞችና ምሁራን የሚያገል ያሰመስለዋል። የኦሮሞን ህዝብ ቅኝ እንደተገዛ አድርጎ ማቅረቡ የኦሮሞ ህዝብ ከሌላዉ ህዝብ ጋር ያለዉን የባህልና የታሪክ ትስስርና የኦሮሞ ህዝብ ለኢትዮጵያ አንድነትና ህልዉና ያበረከተዉን አስተዋፅኦ የሚያሳንስ ነዉ። ከዚህም በተጨማሪ ይህን አይነቱ ትንታኔ አንዱን ማህበረሰብ ጨቋኝ ሌላዉን ተጨቋኝ በማድረግ የሚቀርበዉን የታሪክ ትንታኔ ህያዉ ሆኖ እንዲቆይ የሚፈልግ ያስመስለዋል። ይህም  እስካሁን የሄድንበትን የጋራ አለመተማመን (mutual suspicion) በማስቀጠል ልንፈጥረዉ ለምናስበዉ ዴሞክራሲያዊ ስርአት እንቅፋት ይሆናል።

 

በተለይ በኢትዮጵያን አንድነትና በግለሰብ መብት ላይ የተመሰረተ የፖለቲካ ስርአት እንዲቋቋም የሚፈልጉ ዜጎችን የቀድሞዉ ስርአት ናፋቅዎችና ምኒልካዉያን እየተባለ መስደብ የተለመደ ነዉ። ያሁኑን ተዉልድ የፖለቲካ አስተሳሰብ መተቸት ካስፈለገ በራሱ በትዉልዱ አስተሳሰብ ላይ ተመስርቶ መተቸት ሲገባ ከቀደሙት ስርአቶች ጋር በማያያዝ አንገት ለማስደፋት የሚደረገዉ እንቅስቃሴ ያደባባይ ሚስጥር ነዉ። የዚህ ፅሁፍ አቅራቢ ከወራት በፊት ያደረገዉን የሬድዮ ዉይይት አስመልክቶ የቀድሞዉ ስርአት ናፋቂ የሚል ስድብና ዛቻ የኦሮሞ አክቲቪስቶች ነን ከሚሉ ወገኖች አስተናግዷል። ለዚህም ነዉ የአማራ ወጣቶች ሁሉም የብሄር ድርጅቶች አማራን በጠላትነት የሚፈርጁ በመሆኑ ተደራጅተን እራሳችንን እንከላከል እያሉ ያሉት። ምንም እንኳን ያለፈዉን ታሪካችንን በተመለከተ ብሄራዊ መግባባት ላይ መድረስ አስቸጋሪ ሊሆን ቢችልም እንዲህ አይነት የታሪክ ትንታኔዎችን ለፖለቲካ ፍጆታ ባለመጠቀም የተሻለ የፖለቲካ ድባብ ለመፍጠር ጥረት እንዳልተደረገ ግን ከቀረበዉ ሰነድ መረዳት ይቻላል።

 

ከዚህም በጠጨማሪ የቀረበዉ ሰነድ ባለፉት አስርተ አመታት የብሄረሰቦችን እኩልነት ለማምጣት የተሄደበትን መንገድ፥ ዉጤቱንና ችግሮቹን ሳያነሳ የኦሮሞ ህዝብ ከዛሬ አርባ አመት በፊት በነበረበት ሁኔታ እንዳለ አድርጎ ያቀርበዋል። ከሁሉም ብሄረሰቦች የተወጣጡ ወጣቶች በተማሪዎች እንቅስቅሴ ወቅት ያነሱት የመሬት ላራሹና የራስን እድል በራስ የመወሰን ጥያቄ በደቡብ ኢትዮጵያ የነበረዉን የጭሰኝነት ስርአት ያስወገደ ሲሆን ይህም ለኦሮሞ ህዝብ ታላቅ ለዉጥ አምጥቷል። ደርግም ሆነ ወያኔ ስታሊናዊ በሆነ መንገድ ችግሮቹን ለመፍታት የሄዱበት መንገድ ዉጤቱ አመርቂ ባይሆንም ሙከራዎች ግን ተደርገዋል። ይህ ሁሉ የፖለቲካ ለዉጦች በተካሄዱበት ሀገር አሁንም ቅኝ እንደተገዛን ነን የሚል እድምታ ያለዉ አቀራረብ በጣም ጨለምተኛና  ካላፈዉ ስህተቶች ተምሮ የቀረዉን የእኩልነት ጥያቅ ለማሳካት በሚያስችል መልኩ አለመቀረፁ በኢትዮጵያ ያለዉን አስቸጋሪ የፖለቲካ ሁኔታ ለመፍታት ያለዉን ቁርጠኝነት ዉሱን ያስመስለዋል።

 

የኦሮሞ መሪዎች ስብሰባ ያስፈለገበትን ምክንያት አቶ ጃዋር ሲያስረዳ ወደፊት ለሚደረገዉ የሽግግር ወቅት እያንዳንዱ ማህበረሰብ የራሱን ቻርተር አዘጋጅቶ መምጣት ስላለበት የኦሮሞን ቻርተር  ለማዘጋጀት በማስፈለጉ ነዉ ይላል። ለዚህም የደቡብ አፍሪካዉን ብሄራዊ ኮንግረስና የህንዱ ጃዋራላል ኔህሩ በትግል ወቅት እንዲህ አይነት ቻርተር አዘጋጀተዉ ነበር ሲል ያስረዳል አቶ ጃዋር። እያናንዳንዱ ማህብረስብ የራሱን ቻርተር አዘጋጅቶ ይምጣ ከተባለ  ሁሉም ብሄረሰቦች አንዳንድ ቻርተር በማዘጋጀት ሲመጡ ቢያንስ ከ 80 ያላነሱ ቻርተሮች ተዝጋጅተዉ ሊቀርቡ ነዉ ማለት ነዉ( ያዉም እያንዳንዱ ማህበረሰብ በአንድ ድርጅት ይወከላል ብለን ካሰብን ነዉ።) እንዲህ ያለ ሁኔታን እንዲኖር መፈለግ አላማዉ ዴሞክራሲያዊ ስርአት ወይስ የባቢሎንን ግንብ ለመገንባት ነዉ? ሁሉም ብሄር የራሱን መብት እንዲከበር በሚል በሚያደርገዉ ፍላጎት ሁሉንም የሚያረካ መፍትሄ ማግኘት የሚክብድ ከመሆኑም በተጨማሪ የፈለገዉን ያላገኘዉ ወገን ‘የራሴን እድል በራሴ’ እወስናለሁ ወደሚል ሌላ ዙር ግጭት ይገባል። በተለይ ወታደራዊ ክንፍ ያለዉ የብሄር ድርጅት የሚበረታታ ከሆነ በጉልበት የፈለገዉን ለማድረግ ማንገራገሩ የማይቀር ነዉ። ወያኔም በ1983 ዓም ባደረገዉ የሽግግር መንግስት ምስረታ ወቅት በብሄር የተደራጁትን ብቻ ተቀብሎ ህብረ ብሄር የሆኑትን ግን አልቀበልም ነበር ያለዉ። ለዚህም የተማመነዉ የነበረዉን ጉልበት ነዉ። ኦነግንም ከሽግግሩ መንግስት እንዲወጣ ያደረገዉ ይሄዉ የወያኔ እብሪተኝነት ነዉ። አሁንም በብሄር ተደራጅታችሁ የራሳችሁን ቻርተር አዘጋጅታችሁ ኑ ማለት ተመሳሳይ አካሄድ ያለዉ ነዉ። በርካታ ማህበረሰቦችም በተለያየ ምክንያት ተደራጅተዉ  ቻርተር አዘጋጅተዉ ላይቀርቡ ይችላሉ። በዚህ ጊዜ የነዚህ ማህበረሰቦች እድል ቻርተር አዘጋጅተዉ በመጡት ሊወሰን ነዉ ማለት ነዉ? ይህስ አካሄድ ወያኔ በ1983 ካደረገዉ በምን ይለያል? ወታደራዊ ክንፍ ያላቸዉ የፖለቲካ ሃይሎች እኛ ባልነዉ ካለተስማማችሁ ዞር በሉ ቢሉ ዋስትናዉ ምንድን ነዉ? አልሸሽም ዞር አሉ እንደሚባለዉ ተመልሶ ወደ ግጭት አያስገባንም ወይ?

 

አቶ ጃዋር ያቀረባቸዉ የደቡብ አፍሪካ፤ ህንድና ቱኒዝያ ምሳሌዎች አሁን ከተጠራዉ የኦሮሞ የነፃነት (freedom) ቻርተር ጉዳይ በጣም የተለዩ ናቸዉ። በነዚህ ሃገሮች የቀረቡት የነፃነት (freedom) ቻርተሮች ሆነ ድርድሮች ሃገራዊና የሁሉንም ማህበረሰብ ፍላጎት የሚያንፅባርቁ እንጂ የአንድ ብሄርን ብቻ የሚመለከቱ አልነበሩም። እንዲሁም በህንድ የተካሄደዉ የፀረ ቅኝ ግዛት ትግልና በደቡብ አፍሪካ የተካሄደዉ የፀረ አፓርታይድ ትግል አሁን ኢትዮጵያ ዉስጥ ካለዉ የፖለቲካ ሁኔታ ጋር ያላቸው ዝምድናና እና ልዩነት በግልፅ አልቀረበም ። የምናቀርባቸዉ ምሳሌዎች ተገቢ ትርጉማቸዉን የያዙ ቢሆኑ የምናቀርበዉን ሃሳብ ተአማኒነት ያጠናክረዋል። አቶ ጃዋር ስለ ቱኒዝያ የተናገረዉም እኛ እየሄድንበት ካለው ጋር የሚገናኝ አይደለም። ከሌሎች አብዮት ከተካሄደባቸዉ የአረብ ሃገራት በተለየ የተሻለ የፖለቲካ ሽግግር በቱንዝያ የተፈጠረዉ እንደ ሊቢያና ሶርያ በሃይማኖትና በጎሳ ለመከፋፈል ባለመፍቀዳቸዉ ነዉ። ወታደራዊ ክንፍ ያላቸዉ የብሄር ድርጅቶችን የምናበረታታ ከሆነ ግን ለጊዜዉ በአንድ ጠላት ላይ ሲያተኩሩ ልዩነት የሌላቸዉ የሚመስሉ የፖለቲካ ህይሎች ያ ጠላት ከስፈራዉ ሲነሳ  እርስ በርሳቸዉ መበላላታቸዉ የማይቀር ነዉ።  ሊብያ ዉስጥ በተካሄደዉ አብዮት ወቅት ሁሉም ጎሳዎች ጋዳፊን ለመጣል ሰምና ወርቅ ሆነዉ ከሰሩ በሗላ አሁን ሁሉም በየፊናዉ  ወታደራዊ ቀጠና አቋቁሞ እየተጋጨ ሲሆን ማዕከላዊ መንግስት በስምምነት ለመመስረት አልቻሉም ።

 

በእዉነት የኢትዮጵያን የፖለቲካ ችግሮች ለመፍታት ቅንነቱና ቁርጠኝነቱ ካለ እንደ ኑክልየር ሳይንስ ዉስብስብ ስላልሆነ 80 ቻርተር ማዘጋጀት አያስፈልገዉም። የኢትዮጵያ የፖለቲካ መሰረታዊ ችግሮች እንዴት ብሄራዊ አንድነትንና የብሄር  መብትን፥  የግለሰብና የቡድን መብትን አጣጥመን እንቀጥል፥  እንዴት ብሄራዊ መግባባትን እንፍጠር፥ ዴሞክራሴያዊ ባህልና ተቋማት እንዴት እንገንባና ማህበራዊና ኤኮኖምያዊ ፍትህ እንዴት እናረጋግጥ የሚሉት ናቸዉ። እነዚህን የፖለቲካ ጥያቄዎች ለመመለስ ዋናዉ መነሻ የተናጥል አካሄድን በተቻለ መጠን በማስቀረት ሁሉም የፖለቲካ ሃይሎች በጋራ የሚመክሩበትን ሁኔታ ማመቻቸት ነዉ። ነገር ግን አሁንም የሽግግር ሂደቱን በበላይነት ለመቆጣጠር የሚካሄደዉ ፉክክር ስር የሰደደዉን የፖለቲካ ሃይሎች አለመተማመን እንዲቀጥል የሚያደርገዉ ከመሆኑም በተጨማሪ የግጭትንና የእኔ አውቅልሃለሁን የቆየ የፖለቲካ ባህል ለመለወጥ የሚኖረዉን እድል ያደበዝዘዋል።

ፈይሳና አቶ ኃይለማርያም፤ ፈይሳና ቀነሲሳ

0
0

ከሚኪያስ ግዛው
ፈይሳና አቶ ኃይለማርያም ሁለቱም ኢትዮጵያዊ ናቸው፣ አንዳቸው ከአምቦ፣ ኦሮምያ፣ አንዳቸው ከወላይታ ሶዶ። የሁለቱም ክልል ሕዝቦች ኢትዮጵያዊ ወርቀዘቦ ናቸው። ፈይሳና አቶ ኃማ የእድሜ ልዩነቶች አሏቸው። ፈይሳ ለግላጋ ስፖርተኛ ወጣት ሲሆን እሳቸው ደግሞ ጎልማሳ ምሁር ናቸው። እሳቸው የሃገር መሪ ተብለዋል – እርሱ ደግሞ ስልጣን የለውም። ይህ ሁሉ ልዩነት ተፈጥሯዊ ነው፣ ክፋት የለውም። ልዩነታቸውን የከፋ የሚያደርገው ማንነታቸው አይደለም። አቋማቸው ነው። እርሱ የኢትዮጵያ ሕዝብ አጋር ሲሆን እርሳቸው የትግሬው ነጻ አውጭ ግንባር ተላላኪ ናቸው። እዚህ ላይ ነው በሁለቱ መሃከል የጎላ የስብዕና ልዩነት የሚታየው። ስፖርተኛው ፈይሳ ራሱን መርቶ፣ ራሱ ወስኖ የትግሉ አጋር ሆነ። ሜዳልያ፣ ገንዘብ፣ ዝና ከኢትዮጵያ ሕዝብ ጋር ነው የሚያምረው አለ። ወገኖቼ እየተገደሉ፣ እየተሰደዱ እኔ ፎቅ ለመስራት ብዬ ወደ ሃገሬ አልመለስም፣ ከቶውንስ ምን አገር አለኝና – ብሎ መሰደዱን መረጠ። የተሰደደው ብዙዎች እንደሚሰደዱት ለተሻለ ኑሮ ፍለጋ አይደለም።

አቶ ኃማ ለየት ይላሉ። እርሳቸው የሚናገሩት ሳሞራ ያዘዛቸውን ወይም ስብሃት የነገራቸውን ነው። እጅግ ያሳዝናሉ። አበበ ገላው አንድ ጊዜ “እኔ እሳቸው በጣም ያሳዝኑኛል” ሲል ሰምቻለሁ። አቶ ኃማ እንደ ፈይሳ በራሳቸው አይመሩም። ሁሉንም የኢትዮጵያ መሪዎች ስናይ ራሳቸውን የሚመሩ ወሳኞች ነበሩ። የቅርቡን እንኳን ብንመለከት ኮሎኔል መንግሥቱ ቆፍጣና፣ ወሳኝና ባመኑበት የሚጓዙ ቆራጥ መሪ ነበሩ። አቶ መለስም ቢሆኑ ክፋት፣ ዘረኛ፣ አማራውንና ኦሮሞውን የፈጁ፣ ሙሰኛና ቀማኛ ነው እንጂ ታሪካቸው፣ ከእርሳቸው በታች የነበሩት የአራተኛና አምስተኛ ክፍል ተማሪዎች አይመሯቸውም ነበር።

አቶ ኃማ ተዳፍረው አንድ ነገር ተናገሩ። “ፈይሳን ያታለሉት ውጭ ሃገር ያሉት ኦነጎች ናቸው” ሲሉ። “የማህበራዊ ሜድያውም ለዚህ ሁሉ አስተዋጾ ስለሚያደርግ መዘጋት አለበት” ብለው ለተመደ ተናገሩ። ይህን ፈጽሞ የማይሆን ነገር “እንዲህ ብለህ ተናገር” ብሎ የላካቸው ምንም እውቀት የሌለው ደብረጽዮን ነው። ቢያንስ በምሁርነታቸው እንኳን ሊያከብሯቸው ይገባ ነበር። ደብረጽዮንና በረከት የራሳቸውን መልክ የሚያሳያቸውን የፌስ ቡክ ድረ ገጽ አይወዱትም። ፌስ ቡክ ላይ ቁጭ ብለው የሚውሉት የፌስ ቡኩ ሚኒስቴሩ ዶክተር ቴዎድሮስ አድሃኖም ናቸው። እርሳቸው ፌስ ቡክ እንዲዘጋ አይፈልጉም።

ፈይሳና ቀነኒሳ በብዙ ነገሮች ይመሳሰላሉ። ሁለቱም የኦሮሞ ልጆች የሆኑ ዝናን ያተረፉ ሯጮች ናቸው። ልዩነታቸው ግን ፈይሳ የሚሮጠው እንደ አባባ ቢቂላ ለሃገሩ ሲሆን ቀነኒሳ ደግሞ ለብር ነው። ለንብረቱ ባይፈራ ኖሮ ቃለ መጠይቅ ሲደረግለት ሰው በላውን ወያኔ ሙሉ ለሙሉ አይደግፍም ነበር። ቀነኒሳ ሕዝቡን በማያስቀይም መንገድ ዳር ዳሩን በመሄድ ጥያቄውን ማድበስበስ ወይንም ዝም ማለት ይችል ነበር። ቀነኒሳ ወደ አገሩ እንደሚመለስ ይታወቃል። የግድ ፈይሳ የወሰደው ዓይነት እርምጃ መውሰድ አለበት ማለት አይደለም። ማንም ቢሆን አገሩ የሚመለስ ሰውን “ለምን እንዲህ እንዲህ ብለህ ተቃውሞህን አልገለጽክም” ማለት አይቻልም። ቀነኒሳ በሰው በላዎች ወደ ተያዘችው ሃገሩ ስለሚመለስ እንዳይበላ ለፎቁም ቢሆን መጠንቀቅ አለበት። ይህን ሁሉም ይረዳለታል። ነገር ግን “ስፖርትና ፖለቲካ አይገናኝም” – “ኢትዮጵያ ማንም በነጻነት የፈለገውን መጠየቅ የሚቻልባት ሃገር ነች” ብሎ ሲናገር በእስር ቤት ያሉትን እነ እስክንድርን፣ አንዷለምን፣ ተመስገንን ብቻ ሳይሆን ቁጥር ሥፍር የሌቸውን የራሱ ወገን የሆኑትን የኦሮም ልጆች ሠላማዊ ጥያቄ መታፈኑንና ለዚሁ ሲሉ በእስር መሰቃየታቸው ሳያንስ እዛው እስር ቤት በእሳት የተለበለቡትና በጥይት የተገደሉትን መዘንጋት አልነበረበትም። ምናልባት የንቃተ ኅሊና ወይንም የጥቅም ጉዳይ ሊሆን ይችላል ቢሆንም ግን ተሳስቷል። ስለሆነም “አንበሳ” ተብሎ የተሰጠው ሹመት ይገፈፋል። ፈይሳና ቀነኒሳ ሁለቱም ስማቸው በ”ሳ” ፊደል ስለሚያልቅ “አንበሳ” ተብለው ተዘፍኖላቸዋል። ፈይሳን “አንበሳ” ያለው የኢትዮጵያ ሕዝብ ሲሆን ቀነኒሳን ደግሞ “አንበሳ” ብሎ ያቀነቀነለት ዝነኛው ቴዲ አፍሮ ነው። ቴዲ ያን ጊዜ ቀነኒሳን ሲመለከተው “አንበሳ” ያለው “አንበሳ” መስሎት ነው እንጂ ጉድና ጅራት ኋላ መሆኑን ቢያውቅ ኖሮ ፟ቀነኒሳ – የገንዘብ ቦርሳ” ብሎ ያሞካሸው ነበር። ለምን? እንኳን ብለ ቢጠይቁት ቴዲ ምናልባት– “ቀነኒሳ ብዙ ገንዘብ ለሃገሩ ይዞ ስለመጣ ነው ቦርሳ ያልኩት” – ብሎ ይመልስ ነበር። ሙዚቃ ቅኔ ነች።

d1ddcb26f-1

ፈይሳንና አቶ ኃማ እንዲሁም ፈይሳንና ቀነኒሳን ስናነሳ ምክንያት አለን። አቶ ኃማ በመለስ ተታለው በመሃይሞች መታዘዛቸው ሳያሳዝነን አልቀረም። ለስብሰባ ሲወጡ ጥገኝነት ጠይቀው እውጭ ቅሩ ቢባሉ አልሰማ ብለዋል። አሁን የቀራቸው የእሬቻ ዕለት እርሳቸው ሳያዙ እነ ሳሞራ ባስተኮሱት ጥይት በአግዓዚ ለተረሸኑት፣ በየገደሉ ገብተው ለሞቱትና ሆራ ሃይቅ ለሰጠሙት ልጆች ጸሎት አደርገውና ለሠሩት ኃጢዓት ሁሉ ንስሃ ገብተው ሲያበቁ፣ ከድንጋይ ጋር ታስረው ሆራ ኃይቅ ዘሎ ገብቶ መስጠሙ ነው። ከዚህ የተሻለ አማራጭ የለምና ስጋቸውን ገድለው ነፍሳቸውን ማዳኑ ይሻላል። የሕዝቡ ቁጣ እያየለ ነው።

ራጮቻችን ደግሞ ነገ በርካታ የኢትዮጵያ ልጆች ወዳሉበት ሃገሮች ለሩጫ ውድድር ይጓዙ ይሆናል። የሩጫ ውድድር ብቻ አይደለም። ሌላም ፈተና አለ። የኦሮሞውና አማራው ልጆች ማጨብጨብና ሆታ ብቻ ሳይሆን እጃቸውን ወደ ላይ አጣምረው ሃገር ቤት ያለው ወገናቸውን ሰቆቃ ላለም ሕዝብ ያሳያሉ። ውድ ሯጮች! የወያኔዎቹን ባንዲራ ብትለብሱ የሕዝቡ ሰቆቃ ይወቅሳችኋል። የኢትዮጵያን አንጡራና ንጹሂቷን ባንዲራ ብትለብሱ ወያኔ ሃገር ቤት ስትገቡ ባያስራችሁም እንኳን በሚቀጥለው ጊዜ አይልካችሁም። ምን ይሻላችኋል። ከዚህ ሁሉ ወያኔ እስኪወድቅ ትንሽ ቀን ነች – አመመኝ – ብላችሁ ሩጫውን አቁሙ። ሮቤል እንደለመደው ሄዶ ይሮጣል። እርሱ ቢጮሁበትም ባይጮሁበትም አይገባውም፣ አባቱ ባለሥልጣን ናቸው። ተመልሶ እዛው ከፍልፍሉ ጋር በኢቲቪ ይቀርባል። ሯጮቻችን ግን አስቡበት። ዝና፣ ብር ወይንስ የኢትዮጵያ ሕዝብ? እንደ ጥላሁን ገሠሠ አቋመ ብርቱ ኢትዮጵያዊ ሆናችሁ ሃገር በሞላ – ወገን ከዳር እስከዳር – ተነቃንቆ ቀብራችሁን ቢያሳምርላችሁ ይሻላል።

ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር።

የትግራይ ተወላጆች በሙሉ ከቢሾፍቱ ተጭነው ተወሰዱ |ክንፉ አሰፋ

0
0

በደብረዘይት (ቢሾፍቱ) ይኖሩ የነበሩ የትግራይ ተወላጆች ዛሬ ቅዳሜ(8 ኦክቶበር)ሙሉ በሙሉ ከተማዋን ለቀው መውጣታቸውን በስልክ ካነጋገርናቸው የከተማዋ ነዋሪዎች ማረጋገጥ ችለናል።

የትግራይ ተወላጆቹ ከተማዋን ለቅቀው የወጡት በቢሾፍቱ የኢሬቻ በዓል የሰዎች ሕይወት መጥፋቱን ተከትሎ የአካባቢው ሕዝብ ከጫፍ እስከጫፍ ነቅሎ በወውጣት እያካሀደ ባለው ሕዝባዊ አመጽ ሊመጣ ካለው አደጋ ለማምለጥ ነው። ህወሃት በዜጎች ላይ እየፈጸመ ያለውን ግድያ በከተማዋ ያሉ ሁሉ ሲቃወም የትግራይ ተወላጆች ግን ዝም ማለታቸው ሕዝቡን በእጅጉ እንዳስቆጣው ነዋሪዎቹ ተናግረዋል።

የትግራይ ተወላጆቹ ሃብት ንብረታቸውን እየጣሉ ከተማዋን ለቅቀው ወዴት እንደሄዱ የታወቀ ነገር የለም።

ላለፉት አራት ቀናት በደብረዘይት እንደ አብዛኞቹ ከተሞች የንግድ እና የስራ እንቅስቃሴ ቆሟል። ሱቆች ተዘግተዋል፣ ሕዝብም ከቤቱ አይወጣም። አልፎ አልፎ የከባድ መሳርያ ድምጽ የሚሰማ ሲሆን መንግስታዊ ተቋማት እና ከህወሃት/ኦህዴድ ጋር ንክኪ ያላቸው ተቋማት ወድመዋል።

በናዝሬት መግቢያ የምትገኘው ዱላላ ማርያም ወረዳ የህወሃት/ኦህዴድ ንብረቶች እና ጽ/ቤቶች ወድመዋል። ሊበን ጭቆላ ወረዳ አመራሩ ተነስቶ ወረዳው በሕዝብ እየተመራ ይገኛል። ወንጂ የስኳር ፋብሪካው ብቻ ሳይሆን አገዳውም ሙሉ በሙሉ መቃጠሉን ከስፍራው ያነጋገርናቸው እማኞች አረጋግጠዋል።

ከዱከም አንስቶ እስከ አገረማርያም የሚወስደው የጦር ቀጠና በመምሰሉ ምንም አይነት ተሽከርካሪ ላለፉት 6 ቀናት እንዳላዩ እማኞች በስልክ ተናግረዋል። ከደቡብ መስመር አንጻራዊ ሰላም የሚታየው በአዋሳ ከተማ ብቻ ነው።

በዲላ እና ወንዶገነት የህወሃት ባልሰልጣናት መኖርያ ቤቶች አጋይቶባቸዋል። ባለስልጣናቱ እና ከድሬዎቹ በሙሉ ከተማዎቹን እየለቀቁ ወደ አዋሳ ከተማ ገብተዋል።

በዲላ መስጊዶች እና አብያተ-ክርስትያናት በዛሬው እለት ባልታወቀ ሃይል ወድመዋል። የአካባቢው ነዋሪዎች የህወሃት ካድሬዎች ሆን በለው የሃይማኖት ጸብ ለመቀስቀስ እንዳቃጠሉት ነው የሚናገሩት።

ደምቢዶሎ እና ምእራብ አርሲ የጦር ቀጠና ሆነው መሰንበታቸውን እና በጦርነቱ በርካታ ሰዎች ማለቃቸን የአሜሪካ ድምጽ ራድዮ እማኞችን ጠቅሶ ዘግቧል።

2139583693_b5d9bd563a_b

የአላሙዲን እና የአዜብ መስፍን ንብረት የነበረው ጉመሮ ሻይ ነደደ |ዝርዝር መረጃ

0
0

alamudi
(ዘ-ሐበሻ) ንብረትነቱ የሼህ መሐመድ አላሙዲን እና የወ/ሮ አዜብ መስፍን ንብረት እንደሆነ የሚነገርለት ጉመሮ ሻይ መውደሙ ተሰማ::

የኢሉባቦር አሌ ወረዳ ነዋሪዎች፥ በወረዳቸዉ ከሚገኘዉ ከጉመሮ ሻይ ፋብሪካ፥ በቂ ጥቅም እያገኘን አይደለም ሲሉ ቅሬታቸዉን ባለፈው ግንቦት ወር ማሰማታቸው ይታወሳል:: ነዋሪዎቹ በተለይ ፋብሪካዉ የሰዉ ኃይል ሲቀጥር በቂ ዕድል ለአካባቢዉ ነዋሪዎች እንደማይሰጥና የአዜብ መስፍን ዘመዶችና የዘር ሀረጓ ብቻ እየተመረጠ ይቀጠራል ሲሉ በተደጋጋሚ ሲቃወሙ ነበር::

የጉመሮ ሻይ ልማት ድርጅት በሚድሮክ ኢትዮጵያ የሚተዳደር የግል የሻይ ፋብሪካ ነው ቢባልም የአቶ መለስ ዜናዊ ባለቤት የሆኑት ወ/ሮ አዜብ መስፍንም ባለቤትነት አላቨው:: በዊኪሊክስ የተለቆ የነበረው መረጃ እንደሚያስረዳው ወ/ሮ አዜብና አላሙዲ ይህንን ትልቅ ኩባንያው በ 24ሚሊዮን ዶላር ነው የገዙት:: ገንዘቡን ለመንግስት ይክፈሉ አይክፈሉ ግን የሚታወቅ ነገር የለም::

ባለፈው ሳምንት የ እሬቻን በዓል ተከትሎ ከ500 በላይ ሰዎች በሕወሓት መንግስት መገደላቸውን ተከትሎ ሕዝብ ባስነሳው ተቃውሞ በኤሊባቡር አሌ የሚገኘው ይሄው ጉመሮ ሻይ ዛሬ መንደዱ ተገልጿል:: ጉመሮ ሻይ ባለፈው ግንቦት ወር ላይም በተመሳሳይ በ እርሻው ላይ ቃጠሉ ደርሶበት የነበረ ሲሆን የዛሬው ግን የከፋ ነው ተብሏል::


በሻሸመኔ በተጋድሎ ላይ ያለው ሕዝብ 70 ጠመንጃዎችን ማረከ |የትግራይ ነጻ አውጪ የሚጠቀምባቸው ቢሮዎች ወደሙ

0
0

Zehabesha-News.jpg

(ዘ-ሐበሻ) መሞታችን ካልቀረ እየገደልን እስከነጻነት ድረስ እንሞታለን በሚል የተነሱት የኦሮሞ ወጣቶች (ቄሮ) በሻሸመኔ በትግራይ ነጻ አውጪ ሰራዊት እና ሚሊሻዎች ላይ በወሰዱት እርምጃ ከ70 በላይ የጦር መሳሪያዎችን መማረካቸው ተሰማ::

ወጣቶቹ ባደረጉት ብርቱ ተጋድሎ በተለይም በሻሸመኔ ጀንገላ ወንደሬ በተባለችው ቀበሌ ውስጥ የትግራይ ነጻ አውጪ መንግስት ከሚጠቀምባቸው ቢሮዎች መካከል ከ6 በላይ የሚሆኑት መውደማቸው ተገልጿል::

እንደዘገባዎች ከሆነ በሻሸመኔ ሕዝቡ ከስር ዓቱ ጋር እያደረገ ያለው ተጋድሎ ስር ዓቱን ለአንዴና ከለመጨረሻ ጊዜ ጠራርጎ እስከማስወጣት ነው:: በዚህም መሰረት የተለያዩ ቀበሌዎችን ሕዝብ መቆጣጠር የቻለ ሲሆን የቀበሌ ሰራተኞችም ከሕዝቡ ጋር መሆናቸውን በመግለጽ ላይ ይገኛሉ ሲሉ ለዘ-ሐበሻ መረጃውን ያደረሱ ወገኖች ገልጸዋል::

የሕወሓት ተጨማሪ ውሸት በቢቢኤን ቲቪ ተጋለጠ

0
0


የሕወሓት ተጨማሪ ውሸት በቢቢኤን ቲቪ ተጋለጠ

በዲላ ከ50 በላይ መኖሪያ ቤቶችና 30 መኪኖች ተቃጠሉ |እርስ በእርስ ፍጅቱ ሕዝቡ ከተማውን ለቆ እየወጣ ነው

0
0

dilla-copy
(ዘ-ሐበሻ) በደቡብ ክልል በጌዲዮ ዞን ዲላ ከተማ ሆን ተብሎ የብሔር ግጭት እንዲነሳ በማድረግ የተቀሰቀሰው አመጽ ዛሬም ቀጥሎ ሕዝብ ከተማውን ለቆ እየወጣ መሆኑ ተሰማ:: በዲላ የከብት ማደለቢያና ከ50 በላይ መኖሪያ ቤቶች ሲቃጠሉ ከ30 በላይ መኪኖችም ወድመዋል::

በይርጋጨፌ ከተማም እንዲሁ ንግድ ቤቶች እና መኖሪያ ቤቶች መውደማቸውን የሚገልጹት የዘ-ሐበሻ ምንጮች በከተማዋ የሰዓት ዕላፊ መታወጁን ገልጸዋል::

በዲላና ይርጋ ጨፌ ሆን ተብሎ በጉራጌና በስልጤ ማህበረሰብ ላይ ያነጣጠረ የዘር ጥቃት ተፈጽሟል የሚሉት የአይን እማኞች መስጊድ እና ቤተከርስቲያናት ላይ ሳይቀር ጥቃት መፈጸሙን ጠቅሰዋል:: በዚህ በጌዲዮ ዞን አካባቢ ለ10 ዓመታት ያህል የቆየ ግጭት የነበረ መሆኑን የሚያስታውሱት ምንጮች መንግስት ጉዳዩን ሳይፈታ መቆየቱ ዛሬ እንዲህ ያለው ውድመት እንዲደርስ ምክንያት ሆኗል::

ይህ በ እንዲህ እንዳለ በወናጎ ወረዳ በሌሎች ብሔሮች ንብረቶች ላይ ጥቃት መድረሱን የሚገልጹት የዜና ምንጮች በይርጋ ጨፌ 1 የቡና ሳይት እስከነ ቡናው መቃጠሉ ተዘግቧል:: በጊዴዮ የትግራይ ነጻ አውጪው መንግስት ሆን ተብሎ እንዲህ ያለው የዘር ግጭት እንዲባባስ ለአቅመ አዳም ያልደረሱ ወጣቶችን ማስታጠቁን የሚተቹ ወገኖች አሉ::

የ‘እኔ አውቅልሃለሁ’ ፖለቲካና የኦሮሞ ሕዝብ የመብት ጥያቄ በኢትዮጵያ |ቀነአ ነገሮ (ዶ/ር)

0
0

በኢትዮጵያ ውስጥ የተለያዩ ብሔር ብሄረሰቦችና ሕዝቦች እንዲሁም የተለያዩ እምነት ተከታዮች መኖራቸዉና፤ የእነዚህም ብሔር ብሄረሰቦች የረጅም ጊዜ ታሪክና ባህል፤ ጠቅላላ የሕዝብ ቁጥር፤ የመልክአ ምድር አስፋፈርና የተፈጥሮ ሃብት ይዞታ፤ እንዲሁም ለአገሪቱ ኢኮኖሚ ያላቸው አንጻራዊ አስተዋጽኦ በግልጽ የሚታወቅ ነው። ሆኖም ግን የእነዚህ ብሔር ብሄረሰቦችና ሕዝቦች መሰረታዊ የሰብአዊ መብት ይዞታና ከአገሪቱ ኢኮኖሚ ያላቸው ተጠቃሚነት በእጅጉ የተዛባና አሳዛኝ ሁኔታ ውስጥ ከመሆኑ ባሻገር ፤ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየባሰበት በመሄድ ላይ ይገኛል።
oromia

በኢትዮጵያ ውስጥ በ 2009 አመተ ምህረት 102,443,149 ሕዝብ ይኖራል ተብሎ ይገመታል። ከዚህ ውስጥ 40,977,259 (40%) ኦሮሞ ሲሆን ባለፉት በርካታ አመታት በፖለቲካም ሆነ በኢኮኖሚው ዘርፍ የኦሮሞ ህዝብ ያለው የተጠቃሚነትም ሆነ የአመራር ሚና ካለው ቁጥር ጋር ፈጽሞ የማይመጣጠንና እዚህ ግባ ሊባል የሚችል አይደለም። የኦሮሞ ህዝብ ሰብአዊ መብቱ ተረግጦ፤ ሃብቱ ተዘርፎ፤ ጉልበቱ ተበዝብዞ በኢትዮጵያ ውስጥ የበይ ተመልካች ሆኖ የሚኖር ህዝብ ለመሆኑ ህሊና ላለው ሰው የማይካድ እውነታ ሲሆን ለኦሮሞው በተለይ ግን የዘመናት ሰቆቃ ነው። ሌሎችም ብሔር ብሄረሰቦች የዚሁ እድል ፈንታ ተቁዋዳሽ ቢሆኑም እንኩዋ የኦሮሞን ህዝብ ያህል የችግሩ ሰለባ ናቸው ለማለት አይቻልም።

በተለያየ ጊዜ የተነሱ መሪዎችም ሆኑ የኦሮሞን ሕዝብ እንወክላለን የሚሉ ግለሰቦችና የፖለቲካ ድርጅቶች የኦሮሞ ሕዝብ ውክልና የሌላችውና እኛ እናውቅልሃልን በሚል ብልጣብልጥነትና ድርቅና ሲዘርፉት፤ሲያሰቃዩት፤ሲገድሉት የኖሩና ዛሬም ያሉ መሆናቸው ለቀባሪ እንደማርዳት ያህል ነው። የኦሮሞ ሕዝብ ላለፉት መቶ አመታት በጭቆና ቀንበር ስር ሲማቅቅ የኖረ፤ መሰረታዊ የሆኑ የመብት ጥያቄዎቹ ገና ያልተመለሱና ፤ ይህንንም ቀንበር ለመስበር የሞት ሽረት ትግል በማድረግ ላይ ያለ ሕዝብ ነው::

የኦሮሞ ህዝብ ትናንትናም ሆነ ዛሬ የሚጠይቀው ጥያቄ አንድ ነው። ይኸውም መሰረታዊ ሰብአዊ መብቴ ይከበር ነው። በአገሪቱ ውስጥ በእኩልነት የኢኮኖሚ፤ የልማት፤ የአስተዳደር ወዘተ ተሳታፊና ተጠቃሚ ልሁን፤ አድሎ አይደረግብኝ፤ አልበዝበዝ፤አልፈናቀል፤ ድምጼ አይታፈን ነው የሚለው። ሆኖም ግን በተለያዩ ጊዜያት የተነሱት መንግስታት የሚሰጡት መልሶች ተመሳሳይ ሲሆኑ ሁሉም ‘እኔ አውቅልሃለሁ’ የሚል እድምታ አላቸው። በቅድመ – ሐይለ ስላሴ መንግስታት ኦሮሞ መብቱ መከበር ቀርቶ ኦሮሞ መሆን የሚያሳፍርና ከእንስሳ ጋር በንጽጽር ይታይ እንደነበር ይታወቃል። ያ ማለት ግን አንዳንድ ኦሮሞዎች ባላቸው ከፍተኛ ችሎታ ወይም ከነበረው ስርአት ጋር በመጠጋት ተጠቃሚዎች አልነበሩም ማለት አይደለም። በአንድ ወይም በሌላ መልኩ ግን መሰረታዊው መብታችን ይከበር ብለው የጠየቁ ኦሮሞዎች ከባድ መከራ፤እንግልት፤ ስቃይና እንዲሁም ሞት እንደደረሰባቸው በርካታ ማስረጃዎች አሉ። በሐይለ ስላሴ መንግስትም ቢሆን የኦሮሞ የመብት ጥያቄ መልስ ያላገኘና የኦሮሞ ሕዝብ ከሌሎች ብሔር ብሄረሰቦች ጋር በመሆን ተመሳሳይ ጥያቄ ያነሳ እንደ ነበርና ንጉሱንም ተክቶ የተነሳው ደርግ የኦሮሞን መሰረታዊ የመብት ጥያቄ ችላ በማለትና በመደፍጠጥ ‘እኔ አውቅልሃለሁ’ በሚል ፖለቲካ ያደረሰው ጉዳት የቅርብ ግዜ ትዝታ ነው። በቀደሙት መንግስታት የኦሮሞን ሕዝብ የመብት ጥያቄ ከፍ አድርገው ለማሰማት የታገሉ የኦሮሞ ልጆች በእስር፤ ከመሬታቸው ላይ በመፈናቀል፤ በስደትና እንዲሁም በሞት እንደ ተቀጡ የኦሮሞ ሕዝብ በምሬት የሚያስታውሰው እውነታ ነው።

በወያኔ መንግስትም ቢሆን የኦሮሞ ሕዝብ ለከፋ የመብትና ኢኮኖሚ ዘረፋ እንዲሁም ድህነት ከመጋለጥ በስተቀር መሰረታዊው የኦሮሞ ሕዝብ ጥያቄ መልስ አላገኘም። እንድያውም ቁዋንቁውን በሚናገሩ፤ ባሕሉን በተካኑ፤ የዋህነቱን ባወቁ አስመሳዮች በተለመደው የ ‘እኔ አውቅልሃለሁ’ ፖለቲካ መብቱን ሲረግጡ፤ ሃብቱን ሲዘርፉ፤ መሬቱን ሲወርሱ፤ ልጆቹን ሲገድሉ እያየን ነው።
አብዛኛውን ጊዜ የኦሮሞ ሕዝብ የመብት ጥያቄ ሲነሳ የኢትዮጵያ አንድነት አደጋ ላይ እንደወደቀና በኢትዮጵያ ውስጥ ያሉ ብሔር ብሄረሰቦችም ለአደጋ እንደተጋለጡ የሚያስቡና፤ የኦሮሞ ሕዝብ መሰረታዊ መብት መከበር ስጋት ላይ የሚጥላቸው ወገኖች አሉ። እነዚህ ወገኖች የኢትዮጵያን አንድነት ከኦሮሞ ሕዝብ መሰረታዊ የመብት ጥያቄ በላይ ዋጋ ስለሚሰጡ የኦሮሞ ሕዝብ የመብት ጥያቄ እንደ ስጋት በመቁጠር ሲቻል በ‘እኔ አውቅልሃለሁ’ ፖለቲካ ፤ ሳይቻል ደግሞ በግልጽ የኦሮሞን ሕዝብ የመብት ትግል በመቃወም፤ የኦሮሞን እንቅስቃሴ በማጥላላት፤ የተሳሳተ መረጃ በመንዛት የ‘እኔ አውቅልሃለሁ’ ዜማቸውን ያሰማሉ። ሆኖም ግን የኦሮሞ ሕዝብ የ‘እኔ አውቅልሃለሁ’ አስተዳደር የሰለቸው መሆኑና ያነገበው የዘመናት የመብት ጥያቄ ወደሁዋላ የማይመለስበት ደረጃ መድረሱ በጉልህ እየታየ ነው። ከአሁን በሁዋላ ለኦሮሞ ሕዝብ ተለክቶ የሚሰጥ መብትም ሆነ ስርአት ለኢትዮጵያ አንድነትና የወደፊት ህልውና አደገኛ ነው። በአንጻሩም የኦሮሞ ህዝብ መሰረታዊ መብት መከበር ለወደፊቷ ኢትዮጵያ አንድነትና ህልውና ዋስትና ሊሆን እንደሚችል በመረዳት፤ ሰፊውን የኦሮሞ ሕዝብ ያሳተፈ፤ ጥቅሙን የሚያስጥብቅና፤ መሰረታዊ መብቱን ያለመሽራረፍ ሊያስከበር የሚችል ስርአት መዘርጋት የግድ ነው።

የኦነግ መሪ ዳውድ ኢብሳ ተናገሩ –“ቄሮዎችን በማደራጀት ትግሉን በሃገር ቤት እየመራነው ያለነው እኛ ነን…ለሁሉም ሕዝብ መልዕክት አለኝ”|ሊደመጥ የሚገባው ቃለምልልስ

0
0

(ዘ-ሐበሻ) የኦነግ ሊቀመንበር የሆኑት ኦቦ ዳውድ ኢብሳ ከሰይፈ ነበልባል ራድዮ ጋር ባደረጉት ቃለምልልስ ቄሮዎችን በሃገር ቤት በማደራጀት በአሁኑ ወቅት ወደ ነጻነት እየሄደ ያለውን ትግል እየመራ የሚገኘው እርሳቸው የሚመሩት ድርጅት መሆኑን አስታወቁ:: “እስካሁን ድረስ ትግሉን እኛ እየመራነው እንደነበር ያልገለጽንበት የራሳችን ምክንያት ነበረን” ያሉት አቶ ዳዑድ አሁን ይህን ለምን መግለጽ እንዳስፈለገና ለመላው የኢትዮጵያ ብሔረሰቦች መል ዕክት እንዳላቸው አስታውቀዋል:: ቃለምልልሱ ብዙ ነገሮችን ይነግረናል – ቢያደምጡት ይጠቀማሉ::

dawid-ibsa

Viewing all 15006 articles
Browse latest View live