Quantcast
Channel: Ethiopian News | ዘ-ሐበሻ | Latest News Provider | News For All
Viewing all 15006 articles
Browse latest View live

የወያኔ በዲሞክራሲ ቁማር እስከመቼ? -በአሸናፊ ንጋቱ

$
0
0

በአሸናፊ ንጋቱ

በስልጣን ላይ ያለው የወያኔ መንግስት የዛሬ 22 ዓመት አንግቦት የነበረውን የዲሞክራሲ መፈክር በማየት ዲሞክራሲ የጠማው የኢትዮጵያ ህዝብ የደስታ ጮቤ በመርገጥ ነበር የተቀበለው፡፡ ነገር ግን ይህ መፈክር ድራማ መሆኑ እየዋል እያደረ ነበር እየተጋለጠ የመጣው። ጮቤ እየረገጠ፤ ትግሉን ተቀላቅሎ መስዋት የከፈለውን ህዝብ የቁልቁል ወደ ባሰ የመከራ ማጥ ከቶታል።
Woyanes shoud face justiceወያኔ እራሱ ህግ አውጥቶ እራሱ የማፍረስና በህጉ ያለመገዛት አባዜ የተጠናዎተው አንባገነን ስርአት መሆኑ በሃያ ሁለት አመታት የስልጣን ጉዞው አስመስክሯል፡፡ በትክክል እንደ ህገ-መንግስቱ ቢሆን ኖሮ ህገ-መንግስት የህጎች ሁለ የበላይ ህግ ነው፡፡ነግር ግን ወያኔ ያለምንም ከልካይ እንዳሻው ያለ ህዝብ ተሳትፎ ለስልጣናቸው እርዝማኔ ይመች ዘንድ ሲዘርዙትና ሲደልዙት ይስተዋላል፡፡ ሲፈልግ ስልጣን መብት ሲሰጥህ/ሽ ሳይፈልግ ደግሞ ሲከለክልህ/ሽ በስመ ዲሞክራሲ እየነገደ የሚኖር የማፍያ ስርአት ነው፡፡ የአምባገነን መንግስታት መለዬ በሆነው ሃይልን እየተጠቀመ በመግደል፤ በእስር፣ በመሳርያ እና በዱላ እያስጨነቀ የህዝቡን ስነ ልቦና በማድከም የስልጣን ቆይታውን ማርዘምም የስርአቱ ዋና አላማ፡፡ እንዲህ አይነቱ አምባገነንና በዲሞክራሲ ስም ህዝባችን ላይ ቁማር የሚጫዎት ስርአት ለኢትዮጵያውያችን አያስፈልግም፡፡ ስለዚህ ይህንን በጨካኝኔ የተሞላ ስርአት ከሃገራችንና ከህዝባችን ጫንቃ የምናስወግድበት ሰአት አሁንና አሁን ብቻ ነው።

በዲሞክራሲ ቸነፈር መመታታችን ሳያንሰን አገር አልባ ለመሆን በተቃረብንበት እና ማንነታችን ጥያቄ ውስጥ በገባበት በዚህ ጊዜ ዲሞክራሲን መናፈቃችን ብቻ ተፈጥሮአዊ አያደርገንም፡፡ በተፈጥሮ ያገኘነውን ነፃነት በተግባር ስናስጠብቅ ብቻ ነው፡፡ ይህ ሁሌ ፍዳና መከራ የሆነው በሃገራችን ላይ በጣም ገኖ ከእኔ በላይ ላሳር በማለት በሃይል በጉልበት በስልጣን ላይ በተቀመጠው የወያኔ ስርአት ነው፡፡ የወያኔ ስርአት ስልጣን ከያዘ ቀን ቀንን እየተካ፤ ሳምንት ሳምንታትን እየተካ፤ ወር ወራትን እየተካ፤ አመት አመታትን እየተካ ይኸው እነሆ 22 አመታችንን አስቆጠርን፡፡ በዚህ 22 ዓመት በብዙ ሺህ የሚቆጠሩ ለዲሞክራሲ፤ ፍትና ነፃነት የዘመሩ ዜጎች አልቀዋል፤ ለስደትም ተዳርገው የድራማው ሰለባ ሆነዋል፡፡ አሁንም ዝም ካልነው ሌላ ብዙ አስርት የመከራ አመታትን መጋፈጥ ሊኖርብን ነው፡፡ እስከመቼ ዝም እንደ ምንለው ግን ወገን አይገባኝም፡፡ አሁንም ህፃን፤ ወጣት፤ ጐለምሳና አዛውንት ወገኖቻችን ሲረግፍ፤ ሲሰደዱ ማየት ከሆነ ህልማችን መልካም! ግን ይህንን የሚያልምም ሆነ የሚመኝ ንፁህ ኢትዮጵያዊ ያለ አይመስለኝም፤ ከራሳቸው ከወያኔ ሆዳደር ካድሬዎች በስተቀር፡፡ ስለዚህ ወገኔ ሆይ ይህንን መንግስት ዝም ብለን ልናየው አይገባም፡፡ ወይም እንደ ፈለገ ሊፈነጭብን ቦታ መስጠት የለብንም፡፡ እስካሁን በኢትዮጵያ ህዝብ ላይ ያደረሰው ጭቆናና በደል ይበቃል ልንለው የግድ ነው፡፡

በዲሞክራሲ እጦት ሃገራችንን ማስጨነቁ አልበቃው ያለው ይህ ክፉ ስርአት በአሁኑ ጊዜ የህዝባችንን ኑሮ ከድጡ ወደ ማጡ አድርጎት ይገኛል፡፡ ህዝባችን በኑሮ ውጣ ውረድ ህይወቱ ሰላም አጥቷል። ወያኔ ስርአቱን የሚቃወሙትን ብሎም የዲሞክራሲ ጥያቄን ያነሱ ንፁሃን ዜጐችን መግደል፤ ማሰርና ማሰቃየት መለዬው ነው። ወያኔ ይህን ስትራቴጂ የሚጠቀመው ለሃገራቸው መልካም የሚመኙትን እና ለሃገር ይሰራሉ ተብለው የሚገመቱትን ሃገር ወዳድ ዜጐች ማጥፋት ከመፈለጉ የተነሳ ነው፡፡ ምክንያቱም እነዚህ ሰዎች ሁሌም ለሃገራቸው ደህንነት ለህዝባቸው ኑሮ የሚጨነቁ ስለሆኑ ስርአቱን የመደገፍ ፍላጎት ስለማይኖራቸውና እየፈፀመ ያለውን አረመኔ ተግባር ለህዝብ ሊያጋልጡብኝ ይችላሉ ብሎ ስለሚፈራም ነው፡፡ ታዲያ በዚህ ሁኔታ የሚቀጠለው እንዴት ነው? ውድ ኢትጵያውያን በአሁኑ ጊዜ ህዝባችን ስቃይ ላይ ነው፡፡ ልንደርስለትና ከህዝባችን ጐን ተሰልፈን ነፃነታችን ማፋጠን ይገባናል፡፡

በስተመጨረሻም መጠየቅ የምፈልገው በዲሞክራሲ እየነገደ ያለው ይህ የወያኔ ስርአት በሃገራችን ገነባሁት፤ እያበበም ነው የሚለው የዲሞክራሲ ስርአት የቱ ይሆን?

በየትኛው ዲሞክራሲ፡ ነፃነትና ፍትህ ያለበት ሃገር ላይ ነው አንድ መንግስት ለ22 አመታት ሲገዛ ያየነው? ዲሞክራሲ፡ ነፃነት እና ፍትህ አሰፍናለሁ ብሎ ቃል የገባላትን እናት ሃገር ዛሬ ግን ድንበሯን በመሸራረፍ እየሸጧት፣ እየለወጧት ብሎም ህዝባችንን በኑሮ እሳት ረመጥ እያቃጠሉት፤ ነፃነቱ ቀርቶ የሃገራችንን ህዝቧን እየከፋፈሉ የብሄር ብሄረሰብ መብትን አስከብራለሁ እያሉ እርስ በእርስ ህዝቡን ማጋጨትና ማጨፋጨፉ ይሆን የሃገራችን ዲሞክራሲ መገለጫው?

ነው ወይስ ዲሞክራሲ ለወያኔ ህዝቡን መከፋፈል፣ እንደልብ እንዳይናገር ማፈን፣ መሬትን ያለባለቤቱ ፈቃድ እየነጠቁ መሸጥ፣ ሙስናን ተዋጋሁ እያሉ በሙስና ተጨማልቆ መገኘት፡፡ ይሄ ነው የወያኔ ዲሞክራሲና እና ፍትህ? የቆሰለችውን ኢትዮጵያ አድንሻለሁ ብሎ ለባሰ ህመም መዳረግስ ለምን!? እውነት ግን በተቃራኒው በቁስሉ ላይ እየሸነቆሩ ማድማት ነበር እንዴ አላማቸው? የተራባችሁትን ሰላም እና ዲሞክራሲ እሰጣችኋለሁ ብሎ ቃል የገቡለትን ህዝብ እልል ብሎ ሲቀበል፣ በታሪኩ አይቶት የማያውቀው የመከራ ጦስ መክተት ነበር እንዴ የወያኔ አላማ!? ስራቸውና ተንኮላቸው የገባው/ት ለምን ብሎ ሲጠይቅ/ ስትጠይቅ ወደ ወህኒ እና ወደ ሞት መጣል መሆን አለበት እንዴ የዚያ የምስኪን ህዝብ ለሰራው ውለታ መልሱ? ታዲያ የወያኔ ዲሞክራሲያዊ ግዛት ይኼ ነው?

ዛሬ ህዝባችን የተወለደበትን ምድርና ቀየ በሃይል በማስለቀቅ መሬቱን በኢንቨስትመንት ስም እየተሸነሸነ እየተሸጠ ያለበት ሁኔታ ነው ያለው፡፡ ታዲያ ይሄ ጭቁን ህዝብ ምድሩን ለቆ ወዴት ይሂድ የትስ ይድረስ? ነው ወይስ ስርአቱ ኢትዮጵያን ለማፈራረስ ነው ቆርጦ የተነሳው? ወገኔ ሆይ ሃገር አለን ብለን የምንኮራው መቼ ይሆን? እስኪ መልሱልኝ፤ የቀን ከሌት ጥያቄየና በራሴ መልስም ለማግኘት ባለመቻሌ አንድ ብትሉኝና ለአምሮየና ለመንፈሰይ ሰላምን ባገኝ ነው ለዘመናት የሚመላለስብኝን ጥያቄዎች መሰንዘሬ፡፡ በእኔ በኩል ይህንን አፋኝና አምባገነን ስርአት ያለምንም ልዩነት በአንድ ልብ በቃ ልንለውና፤ በቁርጠኝነት ልንታገለው ይገባል ባይ ነኝ።

ድል ለጭቁኑ ኢትዮጵያ ህዝብ!!!

በአሸናፊ ንጋቱ

ለአስተያየትዎ: andethiopia16@gmail.com የኢሜል አድራሻየ ነው።

 

 

 

 

↧

↧

ስንቶች ሳይኖሩ ሞቱ ስንቶቻችንስ ነን ሳንኖር የምንሞተው? -ጌታቸው ከሰ

$
0
0

ጌታቸው ከሰ/አሜሪካ

(መሪ ቃሉን ፋሲል ተካልኝ ከዚህ ዓለም በሞት ለተለየን ከያኔ አብርሃም አስመላሽ ካቀረበው የግጥም መድብል አንዷን ስንኝ ወስጄ ነው የዛሬውን ጹሑፌ ያቀረብኩት ። ግጥሙን በሙሉ ለማንበብ የዘ-ሐበሻን ድሕረ-ገጽ ከፍተው ያንብቡ።)

እኔ የዚህ ጹሁፍ አቅራቢ በደርግ ዘመነ መንግሥት በአንድ ጊዜ በአራት የወንጀል ዓይነቶች ተጠርጥሬ ታስሬ በልዩ የወንጀለኛ መቅጫ ሕግ 214 ሀ እና ለ ወይም ንኡስ አንቀጽ 23 ተብለው በተጠቀሱ ድንጋጌዎች ይመስለኛል የሞት ፍርድና የእድሜ ልክ ጽኑ እስራት በሚያስቀጣ ወንጀል ተከስሼ ነበር።ቀን የሰጠው ቅል ድንጋይ ይሰብራል እንዲሉ በነዚህ ባለጊዜዎችም እንዲሁ ታስሬ በዋስ ተፈትቼ ጉዳዩ በተንጠልጠል ላይ እያለ ወደዚህ አገር ለመምጣት ችያለሁ። አፍላው የወጣትነት ዘመንና የጉርምስናውን ወቅት እናት አባት ባሉበት ከቤተሰብ ሳይለዩ ከአብሮ አደግና ከሰፈር ጓደኛ ጋር ጊዜን በደስታ ማሳለፈና ለአካለ መጠን ሲደርሱም ዲል ባለ አዳራሽ ወዳጅ ዘመዱ ተጠርቶ ጋብቻ መፈጸም አቅም በሚመጥነው ደረጃ ተመድቦ በመሥራት ወላጅን መጦር ቤተሰብን ማስተዳደር ሀገርን ማገልገል የሚባል ወዘባው ጠፍቶ ይህችን ጥቂት ጊዜ የምንቆይባትን አጭር እድሜም  በትግል ማሳለፍ አንድ አዲስ ትውልድ ተወልዶ ባደገበት አገር በትውልድ ቀየው ለሙያ ሳይበቃ በትምህርት ቤት ሕይወቱን በውል ሳያገናዝብ ጧት ወጥቶ ማታ ለመመለስ ዋስትና በሌለበት የባንዳ ልጆችና ብረት አምላኪዎች ተደራጅተው ሀገር በሚያውኩበት መፈጠርና የተንጠለጠለች ሕይወት ይዞ መኖር መኖር ሊባል ይችላልን? እኔ በሕይወት አለሁ ቢያንስ ያሳለፍኩትን የጨለማ ሕይወት አሁንም ያለሁበትን የባርነት ዘመን ኑሮ መናገር እችላለሁ ሳይኖሩ የሞቱ ሴት እህቶቼንና ወንድሞቼን ሳስብ እጅጉን ልቤ በሀዘን ቀስት ይወጋል።ዜግነቴ ኢትዮጵያዊ- ሀገሬ ኢትዮጵያ-የኢትዮጵያን ሕዝብ የምወድ -ለሀገሬ እድገትና ብልጽግናን የምመኝና የምሠራ -እንዴት በትውልድ ሀገሬ መማር፤መሥራት ፤ንብረት ማፍራት ፤ ቤተሰብ መመሥረትና ቤተሰቤን ማስተዳደር፤ መጦር ያለባቸውን ወላጆቼ መጦርና በነጻነት መኖር ይነፈገኛል?እንደኔ የዜግነት መብታቸው ተገፎ የትውልድ ሀገራቸውን ጥለው እንዲሰደዱ የተገደዱ ፤በሀገራቸውም ሌሊት ከመኖሪያ ቤታቸው እየታፈኑ ቀን ከሚሠሩበት የሥራ ገብታ  እየተዘረፉና በየጎዳናው እየታፈሱ እስር ቤት አጨናንቀው የሚገኙ እህትና ወንድሞቼ እውን በቁማቸው አልሞቱም? ሳይኖሩ መሞት ቢባል ስህተት ሊሆን ይችላልን? ወይንስ ይኸም ኑሮ ነው ሊባል ነው። ? ሕይወትን ለማትረፍ በሚደረግ ጥድፊያ የሰሃራን በርሃ ለማቋረጥ ሲሉ ስንቶቹ  ሕይወታቸውን አጡ ።ስንቶች ኢትዮጵያውያንን የዱር አውሬ በላቸው፤ስንቶችስ ውሃ እንደጠማቸውና መብላት እንደፈለጉ ሞቱ፤ስንቶቹስ በሞት አፋፍ ላይ ይገኛሉ?የወገንን ሕይወት ለማትረፍ እነማን ናቸው ግንባር ቀደም የቆሙት?እውነት ኢትዮጵያውያን ሀገራቸውን ጠልተው ወይም ጠግበው የሚሰድዱ ይመስላችኋል?በፈላ ዘይትና ውሃ የሚቀቀሉት? በየዐረቡ መዲና ጎዳና ላይ በጥይት የሚገደሉትና ፎቅ ላይ ተጥለው ተከስክሰው የሚሞቱት ጠግበው ነው? ህጻናቶቹ የ15ና የ16 ዓመት ወጣቶች ሀገር ጥለው ሲወጡ በሀገሪቱ መዲና አዲስ አበባ ሴተኛ አዳሪነት እንኳን አልሆን ብሏቸው ሲሰደዱ ማንም የዐረብ ውርጋጥ ተቀብሎ ሲማግጥባቸው የሚሰማ ጀሮ የሚያስብ ሕሊና ላለው ይዘገንናል።«ኧረ ጎበዝ እኛን ኢትዮጵያውያንን ምን ነካን? ምን አይነቶቹ  ትውልዶች ነው የተፈጠርን»? ጠግበው እንደወጡ የሚፈርጅባቸው ማን ነው ምን አግኝተው ማን አብልቷቸው ጠገቡና ነው እንዴትስ ጠግበው የተሰደዱ የሚባሉት ኢትዮጵያን የመሰለች ሀገር ያለው ሰው ሀገሩን ይጠላል እንዴ? በጭራሽ ይህ የማይታሰብ ነገር ነው። ይልቅስ ጥሬ ሀቁን እንነጋገርበት ካልን እናንተም እኔም ምሥጢሩን በሚገባ እናውቀዋለን።ምናልባት ይህንም እንደሚሥጥር  ቆጥረነው ከእኛ ለተወለዱት በግልጽ ባለማሳወቃችን ጉዳዩ እንቆቅልሽ  ሊሆንባቸው ይችል ይሆናል ። አሁንም ሌላ ስህተት ፈጸምን ማለት ነው።መረገም ይሉታል ይህ ነው።

ዋናው የችግሩ መንስኤና ተጠያቂው ህወሃትና የህወሃትን ደም የተጣቡ አሁን በሥልጣን ላይ ያሉት ኃይሎች ሲሆኑ ሌሎች ለዚህ ችግር መምጣት የመጀመሪያውን በር የከፈቱ ያደቆኑ ፤ያካኑ ዛሬም ያን ጮማ ምላሳቸውን እንዲያርፍ ያለደረጉ የትውልድ ማለቅ ያጀገናቸው ኤርትራን ያስገነጠሉ፤ህወሃትን እዚህ ያደረሱና በርጅና በህወሃት በር ደጅ እየጠኑ ህወሃትን የሚያበረታቱ የቀደምት የድርጅት አመራሮችና አባላትም በኢትዮጵያ ህዝብ ላይ እየቀለዱ ያሉ መሆናቸው ግልጽ ሊደረግና ሕዝቡ ሊያውቃቸው ይገባል።« በተለይም አማራውንና የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ሃይማኖትን» የኢትዮጵያ ኋላቀርነት፤ ድህነት፤ማይምነት፤የዴሞክርሲ መታፈን፤የዜጎች እኩልነት አለመከበር ምክንያት አድርገው የተነሱና ለኢትዮጵያ አንድነትና በነጻነት ተከብራ እንድትኖር ሳይታክቱ የታገሉትን እየታገሉም እያሉ በሽምግልናቸው እንኳ ርህራሄ ማድረግ ያልቻሉና የገደሉ (ክቡር ቢትዎደድ አዳነ መኮነንን ይመለከታል)፤የካቲት 1966ቱን የሕዝብ እንቅስቃሴ ያስማረኩና ህወሃትን ያነገሱ በስም ሕብረ-ብሔር በተግባር ግን የአማራን ዘር ለማምከን ከጧቱ የተነሱና የዘመሩ የመጡበትን መንገድ መመርመር አሁን ደግሞ መንገዳቸውን አስተካክለው ካልተጓዙ ያችን የጥፋት ካርዳቸውን ማሳየት ብቻ ሳይሆን እንዳለ የድርጅቶችን ተግባር እየመዘዝን መረጃውን እያወጣን ታቀቡ ልንላቸው ዝግጁ ነን።ምክንያቱም አሁን ላለው ትግል ተመክሮውም ሆነ አጠቃላይ መርሁ እጅግ የሚጎዳ በመሆኑ እንጅ ወደ ኋላ ተመልሶ የነገር ቋንጣ ለማመንዥክ ወይም ታግየበት ሳይጠቅመኝ ጉድ አድርጎኝ ቀረ በሚል ስሜት በመገፋትና ፀፀት አይደለም።

ችግርን አለማወቅ አንድ ችግር ሲሆን ችግሩን እያወቅን ችግሩን ማስወገድ አለመቻል ግን የጎርፍ  ውሃ እያሳሳቀ እንደሚወስደው ሰው እየሳቁ እንደመሄድ ነው የሚቆጠረው።

መተማመን ከሌለ እውነት አይኖርም” እውነት ከሌለ ፍቅር አይኖርም” ፍቅር ከሌለ ደግሞ ሰላምና አንድነት አይኖርም” ሰላምና አንድነት ሳይኖር ደግሞ የሚፈለገውን ዓላማ ከግቡ አደርሳለሁ ብሎ ማሰብ የዋህነት ነው።

መተማመን ፦ በአባትና ልጅ ፤ በባልና ሚስት ፤ በወንድማማች ፤ በእህትማማች ፤ በወንድምና እህት ፤ በአክስት አጎት ፤ በቤተዘመድ ፤ በአብሮ አደግ ጓደኛሞች ፤ በቤተክህነት በሚያገለግሉ የሃይማኖት አባቶች ፤ በመስጊድ በሚያገለግሉ ሸኮች ፤ በአንድ ዓላማ በተሰለፉ የድርጅት ሰዎች ፤ በመንግሥት ሥራ ተሠማርተው በሚሰሩ ሰራተኞች ፤ በስቪክ ማህበራት ፤ በንግድ ድርጅቶች ፤ በወታደሩ ፤ በደህንነቱ ፤ በፖሊሱ ፤በግብረ-ሰናይ ድርጅቶች(ኤንጅኦ) ፤ በሙያ ማህበራት ፤ በገበሬው…ወዘተ ከጠፋና የውሃ ሽታ ከሆነ ረጅም ዓመታት አለፉ።

እውነት፦ በአባትና ልጅ ፤ በባልና ሚስት ፤ በወንድማማች ፤ በእህትማማች ፤ በወንድምና እህት ፤ በአክስት አጎት ፤ በቤተዘመድ ፤ በአብሮ አደግ ጓደኛሞች ፤ በቤተክህነት በሚያገለግሉ የሃይማኖት አባቶች ፤ በመስጊድ በሚያገለግሉ ሸኮች ፤ በአንድ ዓላማ በተሰለፉ የድርጅት ሰዎች ፤ በመንግሥት ሥራ ተሠማርተው በሚሰሩ ሰራተኞች ፤ በስቪክ ማህበራት ፤ በንግድ ድርጅቶች ፤ በወታደሩ ፤ በደህንነቱ ፤ በፖሊሱ ፤በግብረ-ሰናይ ድርጅቶች(ኤንጅኦ) ፤በሙያ ማህበራት ፤ በገበሬው…ወዘተ በዓለማችን ከጠፋ ረጅም ዓመታት አለፉ።

ፍቅር፦ በአባትና ልጅ ፤ ባልና ሚስት ፤ ወንድማማች ፤ እህትማማች ፤ ወንድምና እህት ፤ በአክስት አጎት ፤ በቤተዘመድ ፤ በአብሮ አደግ ጓደኛሞች ፤ በቤተክህነት በሚያገለግሉ የሃይማኖት አባቶች ፤ በመስጊድ በሚያገለግሉ ሸኮች ፤ በአንድ ዓላማ በተሰለፉ የድርጅት ሰዎች ፤ በመንግሥት ሥራ ተሠማርተው በሚሰሩ ሰራተኞች ፤ በስቪክ ማህበራት ፤ በንግድ ድርጅቶች ፤ በወታደሩ ፤ በደህንነቱ ፤ በፖሊሱ ፤በግብረ-ሰናይ ድርጅቶች(ኤንጅኦ) ፤በሙያ ማህበራት ፤ በገበሬው …ወዘተ ከተወገደ  ረጅም ዓመታት አለፉ።

ሰላምና አንድነት፦ በአባትና ልጅ ፤ በባልና ሚስት ፤ በወንድማማች ፤ በእህትማማች ፤ በወንድምና እህት ፤ በአክስት አጎት ፤ በቤተዘመድ ፤ በአብሮ አደግ ጓደኛሞች ፤ በቤተክህነት በሚያገለግሉ የሃይማኖት አባቶች ፤ በመስጊድ በሚያገለግሉ ሸኮች ፤ በአንድ ዓላማ በተሰለፉ የድርጅት ሰዎች ፤ በመንግሥት ሥራ ተሠማርተው በሚሰሩ ሰራተኞች ፤ በስቪክ ማህበራት ፤ በንግድ ድርጅቶች ፤ በወታደሩ ፤ በደህንነቱ ፤ በፖሊሱ ፤በግብረ-ሰናይ ድርጅቶች(ኤንጅኦ) ፤በሙያ ማህበራት ፤ በገበሬው…ወዘተ  ከደፈረሰ ረጅም ዓመታት አለፉ።

በነዚህ ምክንያቶች የአገራችን ሉዓላዊነት ማስከበር ሳንችል ቀረን ፤ በእኩልነትና በመፈቃቀር ፤ በመተማመን ላይ የተገነባ አንድነት ለመፍጠር አልችል አልን ፤ ራሳቸውን ከሕግ በላይ ያደረጉ አምባገነን ወራሪዎችን ታግሎ መጣል ሲገባ እጅ መንሳትና አጎንብሶ መሄድን መረጥን ፤ በብዕራቸው ህወሃትን በሚያስጨንቁት ላይ ተሳለቅን ፤ ከህወሃት አፍንጫ ሥር ተደራጅተው እየታገሉ ያሉትን ህወሃት መጠነ ሰፊ ግፍ ሲፈጽምባቸውና ግፉ በዝቶ ሲፈስ ከሚገባው በላይ ሲሄድ እዚህ በላይ ማለፍ አትችልም ቁም ማለት ተሳነን። ይህ ሁሉ የህወሃት ጌቶች በደደቢት ህወሃትን ያደቆኑበት እኩይ መርህ መሆኑን እናውቃለን(ምዕራባውያንና ዐረቦች)። ዳሩ ግን ባርነትን መርጠናልና  በባርነት መኖርን የመረጠው በፈለገው መንገድ መሄድ መብቱ ነው። ጣልቃ መግባትና ማደናቀፍ ግን አይችልም መብቱ የለውም ጉዳዩ የሀገር የኢትዮጵያ ጉዳይ ነውና።ባርነትን አልቀበልም እታገለዋለሁ ያለ ደግሞ ባርነትን ሊያስወግድ የሚችለውን የትግል ስልት አንድነትን ሰንቆ መነሳት የግድ ይለዋል።በውጭ የሚገኘው ስደተኛ ኢትዮጵያዊ በአብዛኛው የመጣበትን ወይም ለስደት ያበቃውን ምክንያት ጠንቅቆ የሚያውቅ ይመስለኛል።በመሆኑም ነው ህወሃት በውጭ ድጋፍ እንዲያጣ ያደረገውና በዓለም ዙሪያ በየመድረኩ እየተሸነፈ የሚወጣው።ይህን ከዕለት ዕለት እንደ ሰደድ እሳት የሚቀጣጠል የሕዝብ እንቅስቃሴ የህወሃት ግብረ በላዎች ወይም በትናንሽ ንግድ ወይም በኮንዶኒየም ጎጆ ተደልለው ለስለላ የተሰለፉ ሊገቱት አለመቻላቸውና የህወሃት ሥርዓት ከመጨረሻው ምዕራፍ ላይ መድረሱን የሚያመለክት ነው።ይህ ሁሉ እየሆነ ያለው ግን እላይ የጠቆምኳቸውን ችግሮች ተሸክሞ እየተጓዘ ነው። እንግዲህ እነዚያን የሰላም የአንድነትና የአብሮነትን መሠረታዊ እንቅፋቶች አስወግደን ብንቀሳቀስ ኖሮ ኢትዮጵያ የትና የት ትደርስ እንደ ነበር መገመት ያዳግትም።እዚህ ላይ የህወሃት ደጋፊዎችን ካነሳሁ ዘንዳ በውጭ ምን እንደሚሠሩ አንዳንድ ግልጽ መሆን ያለባቸውን ነገሮች ማስመር ካለብን ቀደም ብለው በደርግ ዘመነ መንግሥት በሱዳንና ኬኒያ እንዲሁም በሌሎች አገሮች የወጡ፤ በዲቪ የወጡ፤በኢትዮጵያ ኤምባሲ በፓስፖርት የወጡ፤በሀገር ሀብት ለትምህርት የተላኩ ሲሆን በኤምባሲው አማካኝነት በተለያዩ የስቪክ ማህበራት የተደራጁና በየትኛውም የሥራ መስክ በመግባት ለህወሃት መዋጮ በማዋጣት የሚረዱ፤የህወሃትን የውሸት እድገትና ጸረ-ሕዝብ ፖለቲካ የሚያናፍሱ፤በስለላ ተግባር የተሰማሩ፤ጠንክሮ የታገላቸውን በገንዘብ የተለያየ አይነት ጥቃት እንዲደርስበት ማድረግ፤ከሥራ ቦታም ችግሮችን በመፍጠር ሠርቶ እንዳይበላ በማድረግ የተሰማሩ…ወዘተ ሲሆን ሀገር ቤት የሚገኘውን ጥቅምና ጠቀሜታም የሚጋሩ ናቸው።ከባለ ሥልጣናት ጋር የቅርብ ዝምድና ያላቸው የግል ድርጅቶችን በአጭር ጊዜ ከፍተው የከበሩና አሰሪ ከመሆናቸውም በላይ ሀገር ቤት ባለሥልጣናቱ የሚዘርፉትን የሀገር ሀብት የሚያሸሹና በባንክ የሚያስቀምጡ እነዚሁ እኛ መሀል የተሰገሰጉ ትግርኛ ተናጋሪዎችና የሌላው ነገድ አባል የሆኑ ሆዳሞችንም ያካትታል።ስለዚህ እነዚህን ለይቶ ማውጣትና ህዝብ እንዲያውቃቸው ማድረግ ያስፈልጋል።

መቀበል አለመቀበል የእያንዳንዱ የግለሰብ ባሕርይ የሚወስነው ቢሆንም ከ40 ዓመት እና ከዚያ በላይ እድሜ ክልል ውስጥ ያለን(የምንገኝ) ኢትዮጵያውያን የታሪክ ግርዶች፤ሀገራዊ ኃላፊነት የጎደለን፤ግዴታችን የማንወጣ፤ፈሪና ስግብግቦች፤የሌላው ኢትዮጵያዊ ችግርና እንግልት የማይሰማን፤እኛ ላይ ትንሽ ነገር ጎድላ ስናይ ግን ከጋለ ምጣድ ላይ እንደፈሰሰ ዘይት የምንጨረጨር፤ሆዳሞችና የማንጠግብ፤ብልጣ ብልጦች ፤ አስምሳዮችና ውሸታሞች መሆናችን ሳናቅማማ መራሩን በሀገር የማዳንና የመጥፋት ጉዳይ የሚቀርብ ነቀፌታ ወይም ሂስ በፀጋ ልንቀበል ግድ ይለናል።የትግሉ የመጀመሪያ ምዕራፍ ላይ ሊቀመጥ የሚገባው »መፈክርም« ይህ ሊሆን ይገባዋል ብየ አምናለሁ። የቆሸሸ ልብስን ለማጠብ ዝም ብሎ ውሃ ውስጥ መጨመር  የቆሸሸውን ልብስ ሊያጸዳው አይችልም ሳሙና መጨመርና በእጅ ማሸት ወይም ማሽን ውስጥ አስገብቶ እድፉን ማስለቀቅ ያስፈልጋል። እኛም በውስጣችን ያለውን ቆሻሻ ሳናጸዳ ለማስመሰል የምናደርገው የማታለል ስልት መታረም አለበት።የትግሉ እንቅፋት ከመሆን ዝምታም እኮ አንዱ እርዳታ ሊሆን ይችላል።

ከዋናው ጠላት ለመድረስ በመንገድ የሚገጥሙንን እንቅፋቶች ለመጠቆም ብዙ ሀተታ ስለአበዛሁ ይቅርታ እየጠየቅሁ የሀገርና የሕዝብ ጠላት የሆነው ህወሃት የቆመለት ዓላማ መጀመሪያ የተከተለውን መንገድ ኪሱ ውስጥ አስገብቶ ሳያስብ የገጠመውን እድል ማለትም ተገንጥሎ ታላቋን ትግራይ ሪፐብሊክ መቀየስ ሳይሆን እነአዲሱን ኩማና በረከት ተፈራ ዋልዋን እያስመሩ ሀገርን ከጫፍ እስከ ጫፍ መመረሽና መክበር ነበር።ከመክበርም አልፎ አገር መግዛት ተቻለ አገር መግዛት ደግሞ ብዙ ጊዜ ላይሆን ይችላል የሚል ስጋት ነበር 22 ዓመት አሁንም «አብዮታዊ ዴሞክራሲ»የምድር አምላክ ስለሆነ በያንዳንዳችሁ አእምሮ እስኪሰርጥ ሌላ 40እና 50 ዓመት ስጡን ይህን ካልፈለጋችሁ ሰላም አታገኙም እንደ እባብ እራስ እራሳችሁን እያልኩ እፈጃለሁ አለ።እያደረገም ነው።ሌላ-ሌላም ይደረጋል።ምን ይደረግ ዓላማቸው ነውና እነሱ ለቆሙለት ዓላማ ቆመዋል።አልሳካ ሲል ደግሞ የሚበትኑትን በትነው ትግራይ ላይ ለመተከልና የተረፍነውን ለማድማት ያቀዱ ስለመሆናቸው ስጋት ሊኖረን አይገባም።ከዚያ ሁሉ በፊት ግን ኢትዮጵያዊ ነኝ ብሎ የሚያምንና የሚይኮራ የስልጣን ጥማት በሽታ ያልወረረው ኢትዮጵያዊ ወገን ህወሃት ለጥፋት ይህን ያህል ተግቶ ሲሰራ ራሱን በምን ደረጃ ሊመድብ ሊገምት እንደሚችል ሊጠይቅ ይገባዋል።እኛ ታሪክ ልንሰራ አልቻልንም ፤አልሠራንም ቀደምት ወላጆቻችን የሠሩትን ታሪክም መጠበቅና ማስከበር አልቻልንም ለምን?እስኪ ሁላችንም ሊያግባባ የሚችል አንድ ዋናው የችግራችን መንስኤ ይህ ነው የሚል የፖለቲካ ይሁን የታሪክ ተመራማሪ የችግሩ መንስኤ ይህ ነው ይበለን።የፖለቲካ ሥልጣን ፍላጎት፤ዘረኝነት፤ጥቅም ፈላጊነት፤ክብር ፈላጊነት፤ውሸታምነት፤ማናክሎኝነት፤ፍርሃት…ወዘተ ከመሆን አያልፍም ብየ በግሌ አስባለሁ።ህወሃት ግን አንድ ነገር ብቻ ዓይወድም ይፈራል። እሱም አንድነትን ነው።ህወሃትን አንድነት የሚያስበረግገው ጉዳይ ከሆነ ለምን አንድነት አንፈጥርምና ህወሃት ገደል እንዲገባ አናደርግም? ማንኛውም ኢትዮጵያዊ ያነሳው አንገብጋቢ ጥያቄም ይኸው የአንድነት ጥያቄ ነው።ዳሩ ግን የተቃዋሚ ኃይሎች፤የእምነት ተከታዮችና የሃይማኖት መሪዎች፤የስቪክ ማህበራት የባሰውን ሕዝቡን በመከፋፈል የጎላ ሚና ተጫወቱ እንጅ አንድነትን ሊያመጣ የሚችል ለም የሆነ ንጣፍ ሲመሰርቱ አልታዩም። ችግርን በውይይት የመፍታት ባህላችን ኋላ ቀር በመሆኑ ምክንያት ህወሃት 22ኛውን አንገት አስደፊ አገዛዝ አገባዶ ወደ ሌላኛው ዓመት እያኮበኮበ ይገኛል።የሚገርመው ግን በህዝብ አንቅሮ የተተፋና ውስጡ በችግር የተወጠረን ድርጅት መታገልና ማስወገድ አለመቻላችን ነው።ሕዝብ በያለበት ሆኖ ይጮኻል ግድያው አፈናው፤እሥራቱ ቀጥሏል ከአንድ አካባቢ በመጡ ጥቂት ጠባቦችና ጎጠኞች።ተቃውሞውም በተናጠል ቀጥሏል።ወደ ተግባር ሊለወጥ ግን አልቻለም።ህወሃት የተቃዋሚውን ሆነ የሕዝቡን የልብ ትርታ በማዳመጥ ዝምታ እንዲሰፍን ተራ በተራ በነገር እየተነኮሰ ማስተንፈሱን አላቆመም።የሚፈራው አንድነት እንዳይመጣ የሚችለውን ሁሉ እያደረገ ሲገኝ እኛ ግን ህወሃትን ማስፈራራት እንኳን አልቻልንም።ዋናው ችግርም ፍላጎታችን የሥልጣን እንጅ የሕዝብን ጩኸት መሠረት ያላደረገ ከመሆን አይዘልም።ለወር ያህል የቀጠለውና አሁንም መፍትሄ ያላገኘው በሳውዲ አረቢያና አካባቢ የዐረብ አገሮች በኢትዮጵያውያን ወገኖቻችን ላይ እየተፈጸመ ያለውን ዘግናኝ አስገድዶ መድፈር፤ጎዳና ላይ ገድሎ መጎተት፤በሰይፍ መታረድ፤በርሃብና ውሃ ጥማት በበሽታ ማሰቃየት በጅምላ እስር ቤት መታጎር ምክንያት በውጭ ያሉ ኢትዮጵያውያን ቁጣቸውን በተለያየ መንገድ ማሰማት ሲችሉ በሀገር ቤት በሰማያዊ ፓርቲና አንድነት የሞከሩትን ተቃውሞ ማሰማት ህወሃት አያገባችሁም ብሏል።ሌሎች ድርጅቶች ደግሞ ትርፍ ፍለጋ ሲራወጡ ይስተዋላል።ወከባውን ለማርገብ ህወሃት ኢትዮጵያውያን ወደ ሀገራቸው እየተመለሱ ነው ይበል እንጅ እውነታው ሌላ ነው።ኢትዮጵያውያን ኢትዮጵያ አገራቸው ብትሆንም አዲስ አበባም ሆነ ሳውዲ ዐረቢያ በተመሳሳይ መንገድ እንደተያዙ መዘንጋት አይኖርብንም።ሀገርን ጥሎ ለመሰደድ ተቋም አደራጅቶ የሸጠ ህወሃት ነው።ከሳውዲ መንግሥት ጋር ተባብሮ እልቂት ያወጀውም ህወሃት ነው።ስለዚህ ንግዱን ትተን መጀመሪያ አስከፊውን ስአርት ማስወገድና ከዚያ በኋላ ደግሞ ንግድ ያሰበውም ሆነ ወንበር የፈለገው እንደፍላጎቱ ለመሆን ሊንቀሳቀስ ይችላል።አሁን የነብስ አድን ጉዳይ ስለሆነ ሁላችንም አቅሙ በፈቀደልን መጠን ለወገን እንድረስለት።በመጨረሻም ይህችን መጣጥፌን ስሞነጫጭር አንድ ዜና ሰማሁና ብዙ ነገሮች ወደ ኋላ ውስደውኝ ትዝ አሉኝ።በሽግግር ወቅት እንበለው ጠቅላይ ሚንስትር የነበረው ታምራት ላይኔ በሲቢየስ ራዲዮ ኢንተርቪው ሲደረግ አዳምጨ የተዳፈነው ሁሉ ሊጎለጎል ነው ብየ አስብኩና ይህን ሰው ቀረብ ብሎ ማነጋገር ከተቻለ ኢትዮጵያን ከዚህ ያደረሰው ጉዞ ምን እንደሆነ ፍንትው አድርጎ ሊያሳየን ስለሚችል ከተቻለም ሌላውን ያሬድ ጥበቡንም ጨምሮ አፍነው የያዙትን ምሥጢር እንዲተነፍሱ ማድረግ በጣም አስፈላጊ ሆኖ ይታየኛል በተለይ አገር ወዳድ ኢትዮጵያውያን ኢህዴንን አንቀበልም ብለው ህወሃትን የመረጡበትና ህወሃት የኢህዴንን ዶክመንት የጠለፈበት ታሪክ አሁን ለደረስንበት የሀገር ጥፋት ምንጩ እዛ ላይ ስለሚነሳ።

በቸር ይግጠመን

ኢትዮጵያ በክብር ለዘላለም ትኑር!!

ጌታቸው ከሰ/አሜሪካ

 

 

 

       

                    1/ወንጀለኛው ዳኛ ፦

 

ዳኛ የለም እንጅ ቢኖርማ ዳኛ

እጁን አስሮ እግሩን በመጫኛ?

ዳሩ ዳኛ የለም

ቢተውት ግድ የለም።

—ወንጀለኛው ዳኛን የጻፉት ክቡር ሐዲስ ዓለመየሁ ሲሆኑ እነዚህን ስንኞች ሁልጊዜ የተዛባ ነገር ስመለከትና ውስጤ ሲከፋ የማጉረመርምበት በመሆኑ አገራችን ዳኛ እስከምታገኝና የሕግ የበላይነት እስከሚከበር ድረስ ይህን የወሮ በላና የወራሪ ሥርዓት እስከምናስወግድ ድረስ እንዲህ እያጉረመረምኩ ትግሌን እቀጥላለሁ እንጅ ዳኛ የለምና ህወሃትን ታግሎ መጣል መተው አለበት አላልኩም። ወንጀለኛው ዳኛ ብለው የጻፉት ክቡር አቶ ሐዲስ ዓለመየሁም ዳኛ የለም ብለው ተስፋ አልቆረጡም ነበር። መሪና አታጋይ የሆኑ መጽሐፍትን በመጻፍ በወቅቱ የነበረውን ሥርዓት አስከፊነት ፍንትው አድርጎ በማሳየት አስነበቡ አሳወቁን እንጅ።

እህህ! ሀገሬ እህህ! ሀገሬ ሀገሬ ኢትዮጵያ

ሳልኖርብሽ ብሞት ጥፋቱ የማን ነው መቼ ኖርኩብሽና መቼ አይቸሻለሁ

አንች እየናፈቅሽኝ ሀገር እንደሌለው በየባዕዳው አገር እንከራተታለሁ

አራቱን ማእዘን ጓዳ-ጉድጉዳሽን ዘልቄ ሳላየው

የኔውስ እድሌ ተሰዶ መኖር ነው

አወይ ስደት ክፉው ሁሉ ይመኘዋል

እንደኔ ቢቀምሰው መቼ ያስበዋል

አንች ሀገር ኢትዮጵያ ሞኝ ነሽ ተላላ

የደማልሽ ሲጋዝ ያደማሽ ሲበላ

አወይ ጊዜ ሞኙ ስንቱን አጃጃልከው

አንዱን ከፍ አንዱን ዝቅ ማለቱ ሳያንሰው

እንዴት ባገሩ ላይ መኖሪያ ያጣል ሰው

ተው እናንተ ሰዎች እሱ ነው ድንበሩ

ሁሉ ዘራፍ ካለ ይጠፋል ሀገሩ

ስማኝ አንተም እንደሌላው አፈር ትለብሳለህ አፈር ትሆናለህ

ድንጋይ ተንተርሰህ ትቢያም ትሆናለህ

እመነኝ ካንተጋር ተጣልተህ

በፍርሃት ተውጠህ

ቅዥቱ በዝቶብህ

በሀሰት መስክረህ ይገደሉ ያልከው

»           »     ይታሰሩ ያልከው

በሐሰት መስክረህ ይሰደዱ ያልከው

»            »      ይራባቸው ያልከው

ሀገሬን ለመሸጥ ፊርማ ያሰፈርከው

ሕዝቤን ለመጨረስ ምክር የመከርከው

ጥቁር ካባ ለብሰህ ሐሰት የፈረድከው

ፍትሕን አዛብተህ ሕጉን ያፈረስከው

ወንጀለኛው ዳኛ ለሆድህ ያደርከው

የኮተቤው ዳኛ ለሆድህ ያደርከው (ኮቴቤ የህወሃት ዳኞች መፈልፈያ ፋብሪካን ይመለከታል)

ፍርድ እየገመደልክ ስንቴ ልትኖር ነው?

እምነቴን እንዳጣ ነገድ እንዳይኖረኝ

ትውልድ እንዳልተካ ዘርም እንዳይኖረኝ

ሀብት እንዳላፈራ ድኻ ልታደርገኝ

ዜግነቴ ጠፍቶ ሰንደቄን እንዳላይ

የሀገሬ የጥንት አባቶቼ ታሪክ እንዳይታይ

ባህል ወግ ልማዴ ቅርሴ እንዳይታወቅ በዚህች ምድር ላይ

አብረን እንዳንወግን እኛን ልትለያይ

ነገር ስታሻኩት ጥላቻን ስታምጥ

አገር ልታጠፋ ሕዝቤን ልትበጠብጥ

ቆላ ደጋ ስትል በየአገሩ ስትሮጥ

ክፉ ቀን ተጣራ ወዴት ልትገባ ነው

ምላስህ ሊታሰር ልሳንህ ሊዘጋ እየተጠራህ ነው

ጦሩ ሲመክትህ ገንዘቡ ሲያወጣህ ደህንነት ሲያድንህ

እኮ እናይሃለን እብሪቱ ትቢቱ ከመሞት ሲያድንህ

Pen

↧

ዶክተር ቴወድሮስ አድህኖም በእውነት አዝነው ወይስ መስታወቂያ እየሰሩ !!

$
0
0

Gebregziabher Lema /Kitzingen/

tewedros adhanom with returneesየኢትዮጽያ ህዝብ  የሞተበት፤ ያዘነበት፤ ፍትህ ያጣበት ፤የተራበበትና የተሰደደበት ግዜአቶች ቢኖሩም   አሁን ግን እራሳቸው ከሚያደርሱብን ግፍና በደል  በተጨማሪ በባእዳን ሀገራት    ተደፍሮና ተነክቶ የማያውቀው ህዝብ   አሁን ባለው  ስርአት  ታሪካችንንና መንነታችንን  ለመጥፋት መጠነ ሰፊ ዘመቻ እየተካካሄደብን ነው። ይህ የማንነታችን መደፈር ዛሬ በገሀድ ወጥቶ ሁላችንም እንስማው እንጅ  ቀደም ሲል ከእኛ በታች በነበሩ የጎረቤት ሀገራት በነጂቡቲ ፤ሱዳን ና ኬንያ ተዋርደንና ተጠቅተን  እንድንኖር ከተደረገ  ውሎ አድሮአል  ። ዛሬ በኢትዮጽያ ህዝብ ጀርባ  ህልውናዋ የቆመው በጂቡቲ እንኮ ኢተዮጺያዊነት ተወርዶ  በነሱ ስንገደል ፤ስንታሰር፤ ሴት እህቶቻችን የነሱ መጫወቻ ሲሆኑ፤ ሹፌር ወንድሞቻችን በራሳቸው ላይ በደል ተፈጽሞባቸው እራሳቸው ተቀጭ ፤በንብረቶቻቸው ላይ አደጋ ተፈጽሞባቸው እራሳቸው ከፋይ ፤ግመሎቻቸውና ፍየሎቻቸው ላይ አደጋ ቢደርስ  ገና ውደፊት እሰከምትወልደው የልጅ ልጅ እዲከፍሉ በማድረግ  ለሚደረገው ህገወጥ ስራወች ሁሉ ለወያኔ አቤት ያልተባለበት ግዜ የለም  የገንዘብ ኪሳቸውን  ለመሙላት ሲሉ ህዝብን  ለባርነት ዳርገውት ይገኛሉ።

ታዲያ ዛሬ ቴወድሮስ አድህኖም ያዞ እንባውን ከየት አመጡት  ምን አልበት በሳውዲ መንግስት ከወገኖቻችን  አላግባብ የፈሰሰው ደም ፤  በቃየል ላይ እንደ መሰከረበት የአቤል ደም ሆኖባቸው ይሆን ? ወይስ  ለሚቀጥለው  ምርጫ  የቢል ቦርድ  ማስታወቂያ  ፎቶ  እያዘጋጁ ? አዎ ይህ ነው እንጂ ካልሆነማ  በስደት  በመንገድ ላይ በየኮንተቴይነሩ ለሚያልቁት ፤በሱዳን፤በጂቡቲ፤በየምን ና ኬንያ በባርነት ያሉ ወገኖች ፤ በሀገራቸው በክልላችሁ ሂዱ ተብለው   ሀብት ንብረት ካፈሩበትና ወልደው ከዳሩበት አያት ቅድምአያቶቻቸው  ለነጻነት አጥትና ደማቸውን ከገበሩበት ሀገርና ቀየ ያንተ አይደለም ተብሎ ሲፈናቀሉ ሌሎች ዘመዶቻቸው እንደጀብድ ሲያወሩት እንደነበር አያውቁም ? ስለዚህ ይህ የውሸት እንባ የኛን አንጀት ያጠነክራል እንጂ የሚያለሰልሰው ፈጽሞ አይሆንም።

↧

ወደ ሳኡዲ አደንዛዥ እጽንና መጠጥን ለማስገባት የሞከሩ ሰዎች ተያዙ ከመካከላቸዉም አንዱ ታጣቂ ተገደለ ተባለና በሰዎቹ ማንንነት ላይ ኢትዮጵያዊ የሚል ታፔላ ተለፈጠበት ለምን?

$
0
0

ምኒልክ ሳልሳዊ

Sadityህወሃት የራሱን ሰዎች በጣም ይፈራል፤ከሌላዉ ኢትዮጵያዊ ወገናቸዉ እንዳይገኛኙም በጣም ይጥራል፤ህወሃት ስልጣኑንን ከለቀቀም ከሰሜን የኤርትራ ህዝብና ከትግራይ ዉጪ ያለዉ ኢትዮጵያዊ የትግራይ ተወላጆችን እንደሚያጠቃም ይስፈራራል።

ህወሃት የለዉጥ ብስራትን የሚሹ የትግራይ ልጆች ኤርትራ ካለዉ የተቃዋዊ ሐይል ጋር ያብሩብኛል የሚልም ስጋት ስላለዉ የትግራይ ወጣት ይሰደድ ዘንድም ሁናቴዎችን ሲያመቻች ቆይቷል። ስለዚህ ብዙ የትግራይ ወጣቶች በየመን አድርገዉ በሳዉዲዋ የጀዛን ግዛት ወደ ሳኡዲ በመግባት ወደ ተለያዩ ከተሞች ተበታትነዋል።ለሳኡዲ ባህልና ሐይማኖታዊ ህግ በቂ የስነልቦና ግንዛቤ የሌላቸዉ ወጣቶችም ያገሪቱን ህግ በመጣስ በኢትዮጵያዊነት መለዮ ላይ ቀዉስን ፈጥረዋል የሚል ቅሬታ ይደመጣል።

በተለይ በሪያዷ የመንፉሃ ክፍለ ከተማ በመጠጥና በአደንዛዥ እጽ ህገወጥ ስራ ላይ የተሰማሩት ወጣቶች በህወሃት ፖለቲካዊ እኩይ ተግባር ሰለባ የሆኑ ለመሆናቸዉ መረጃዎች መዉጣት ከጀመሩ አመታት ቢቆጠሩም ችግሩ ገንፍሎ አንባገነናዊዉ የሳኡዲ መንግስት ዜጎቹ ያነጣጠሩበትን የለዉጥ ኢላምን አቅጣጫ ለማስቀየር እስኪጠቀምበት ድረስ ሃይ ባይ አልነበረም።ይህ ጥቂት ኢትዮጵያዉያን የተሰማሩበት ህገወጥ ተግባር ያለ ሳኡዲ የደህንነትና የህግ አስከባሪ ሐይላት ትብብር እዉን ያልሆነ በመሆኑ የሳኡዲ መንግስትም ከተጠያቂነት አይድንም። ሳኡዲ ዉስጥ ካለዉ ኢትዮጵያዊ ቢያንስ ዘጠና ስምንት ከመቶዉ ለፍቶ አዳሪ ሲሆን በጣም ጥቂት የሆነዉ ኢትዮጵያዊ ባቋራጭ እድገትን ፈላጊ የሚሆንበት አጋጣሚ ይታያል።

ስደተኛ ወይም ስራ ፈላጊ የሆኑ ኢትዮጵያዉያን በነቂስ በሳኡዲ ዜጎች  ጥርስ መግባታቸዉ፣መደብደባቸዉ፣መገደላቸዉ፣የአስገድዶ መድፈር ሰለባ መሆናቸዉ የሳኡዲ መንግስት እራሱ ላወጣዉ ያገሩ ህግ  ወይም አለማቀፋዊ ህግ ደንታ የሌለዉ መሆኑን ፍንትዉ አርጎ ያሳያል። የሳኡዲ መንግስት ለፈጸማቸዉ ኢሰብዓዊ ተግባራት ተጠያቂ ከመሆኑም ባሻገር የደም፣የሞራል፣የጉዳትና የሰራተኞችን የልፋት ዋጋ በካሳ መልኩ እንዲከፍል ኢትዮጵያዉያኑ በጋራ ሊሰሩበት የሚገባ አንገብጋቢ ጉዳይ ነዉ።

ኢትዮጵያዉያኑ በሳኡዲ የደረሰዉን ግፍ ለመታደግ በመላዉ አለም ያሳዩት እምርታዊ ተቃዉሞ እሰየዉ የሚያስብል ቢሆንም፤በየሰልፎቹ መሃከል በጥቂት የጥላቻ አቀንቃኞች የታየዉ ጸረ-ኢስላምና ጸረ-አረብ አቋም የኢትዮጵያን ህዝብ በቢሊዮን ከሚቆጠሩ የአላማችን ዜጎች ጋር የሚያጣላ ሃላፊነት የጎደለዉ ተግባር በመሆኑ ከፋፍሎ የሚገዛዉን ህወሃትን ከመጥቀም ባሻገር ፋይዳ አይኖረዉምና ካማረዉ  የአንድነት ማሳ ላይ የጥላቻዉን አረም ማረሙ ተገቢም ነዉ።

ኢራን ከሳኡዲ አረቢያ ጋር ስር የሰደደ ፖለቲካዊና መልከ-አምድራዊ የሆነ ታሪካዊ  ባላንጣነት አላት። እንደ አንዳንድ የሳኡዲ የመገኛና አዉታሮች አገላለጽ በኢራን የተመለመሉ ኢትዮጵያዉያን ደህነቶች በሳኡዲ አረቢያ ዉስጥ ይገኛሉ የሚል ስጋት አለ። ስጋቱን የሳኡዲ መንግስት ሆን ብሎ የፈጠረዉ ሊሆን ቢችልም፤ የራሱን የዉስጥ  ቅዋሜ ለማርገብ የሚኳትነዉ ህወሃት የለዉጥን ብስራት ፈላጊ የሆኑ  ወጣቶችን ለመሰል ተልእኮ አሳልፎ አይሰጥም ለማትም አዳጋች ይሆናል።

ሁለት አንባገነናዊ ስርዓቶች በጥምረት አንባገነናዊ ተዉሳክን ለማስረጽ ሲዳክሩ፤ በመሃል የሚጠቁትን ኢትዮጵያዉያን ለመታደግ ፍቅር፣አንድነት፣ትብብር ያሻልና በሳኡዲ የሚንቆረቀረዉን የወገን እንባ አባሽ እንሁን። ልብ ያለዉ ልብ ይበል!

 

 

 

↧

ቴዎድሮስ አድሃኖም ቢያጥቡት የማይጠራ ወያኔ ነዉ (ኤፍሬም ማዴቦ)

$
0
0

ኤፍሬም ማዴቦ

tewedros adhanom with returneesየኢትዮጵያ ህዝብና እናስተዳድረዋለን የሚሉት አምባገነን ገዢዎቹ ተስማምተዉና አንዱ ሌላዉን አክብሮ የኖረበት አንድም የታሪክ አጋጣሚ የለም። የእስከዛሬዉ ታሪካችን ምዕራፍ በጥቅሉ ሲታይ ታሪካችን የሚቋጨዉ ህዝብ ተረገጠ፤ ተጋዘ፤ ገዢዎች ደግሞ ረገጡ፤ገዙ፤ አሰሩ፤ አጋዙ እየተባለ ነዉ። አዎ! የኢትዮጵያ ህዝብ እስከዛሬ ባለዉ ታሪኩ ተግዟል፤ ተረግጧል፤ ተንቋል፤ ተንቋሿል። የዘንድሮዉ በተለይ ባለፉት ሁለትና ሦስት ሳምንታት እየደረሰብን ያለዉ ብሄራዊ ዉርደትና ንቀት ግን ታይቶም ተሰምቶም የማይታወቅ ልዩ ከልዩም ልዩ ነዉ። በቀዳማዊ ኃ/ሥላሤ ዘመን የኢትዮጵያ ህዝብ ልክ እንደዛሬዉ ሰብዓዊ መብቱ ተረግጧል፤ ፍትህ ተነፍጓል፤ ነጻነቱን ተገፍፏል፤ ሆኖም አገር ዉስጥም ከአገር ዉጭም ፈላጊና ባለቤት አንደሌለዉ የቤት ዉስጥ እንስሳ የወገንም የባዳም እጅ አልተረባረበበትም። አንገፍግፎን አንፈልግም በቃ ብለን ያስወገድነዉ የቀዳማዊ ኃ/ሥላሤ ስርዐት በስልጣን ላይ በነበረበት ግዜ “ኢትዮጵያ” የሚለዉ ስምና “ኢትዮጵያዊነት” አገር ዉስጥም ሆነ አዉሮፓ፤ አሜሪካና አፍሪካ ዉስጥ እጅግ በጣም የተወደደና የተከበረ ስም ነበር። ዛሬ ወያኔ ነጻ አወጣኋችሁ፤ እኩልነት አመጣሁላችሁ እያለ በሚሰብክበት ዘመን ግን የኢትዮጵያ ሀዝብ አገር ዉስጥም በዉጭ አገሮችም ባለቤት አንደሌለዉ ፈረስ ማንም የሚጋልብበት ፈላጊ እንደሌለዉ  ዕቃ ያገኘ ሁሉ እንዳሰኘዉ እጁን የሚያሳርፍበት የተናቀ ሀዝብ ሆኗል። ለመሆኑ ለምንድነዉ ኢትዮጵያዊነት እንደዚህ  እንደ ተራ ዕቃ የቀለለዉ? ኢትዮጵያዉያንስ ለምንድነዉ በየሄዱበት እንዲህ አይነት ዉርደትና ስቃይ የሚደርስባቸዉ? መልሱ ቀላል ነዉ። “ባለቤቱን ካልናቁ አጥሩን አይነቀንቁ” ወይም  “ባለቤቱ ያቀለለዉን አሞሌ ባለዕዳ አይቀበለዉም” ነዉ።

የወያኔ አገዛዝ እኛ ኢትዮጵያዉያን “ኢትዮጵያዊነት” እያልን ስለምንሳሳለትና ስለምንከባከብለት ትልቅና ክቡር ሀሳብ በፍጹም ግድ የለዉም። እንዲያዉም ወያኔ ሽንጡን ገትሮ ከሚታገላቸዉ ዋና ዋና ብሄራዊ እሴቶቻችን ዉስጥ “ኢትዮጵያዊነት” የመጀመሪያዉ ነዉ። ስለዚህም ነዉ ባለፉት ሃያ ሁለት አመታት በግልጽ እንደተመለከትነዉ “ኢትዮጵያዊነት”  ብለዉ የተጣሩ፤የጮሁ፤ ህዝብን ያስተማሩና የታገሉ ግለሰቦች በወያኔ እየተለቀሙ የታሰሩትና የተገደሉት። ከአገር ዉጭም ቢሆን በየዉጭ አገሩ የሚገኙት የወያኔ ኤምባሲዎች ኢትዮጵያዉያን ከአገራቸዉ ዉጭ ማግኘት የሚገባቸዉን የዜግነት አገልግሎት የሚሰጡት ዜግነታቸዉን እያዩ ሳይሆን ቦንድ የገዛ ያልገዛ፤ “ልማታዊዉን መንግስት” የደገፈ ያልደገፈ እያሉ ወይም “የወርቃማዉ ዘር” አባልነቱን እያጣሩ ነዉ። እነዚህንና ሌሎችም እነዚህን የመሳሰሉ ሰንካላ የወያኔ መስፈርቶች ያላሟሉ ኢትዮጵያዉያን አገር ዉስጥም ከአገር ዉጭም ወያኔ በዜግነት ሳይሆነ በጠላትነት የሚመለከታቸዉ ሁለተኛና ሦስተኛ ደረጃ ዜጎች ናቸዉ። ዛሬ ከአፍሪካ፤ ከኢሲያና ከላቲን አሜሪካ አገሮች ስራ ፍለጋ ሳዑዲ አረቢያ ከሄዱ ዜጎች ዉስጥ እንደ ኢትዮጵዉያን እጁንና እግሩን ታስሮ የተገረፈ፤ እንደሴቶቻችን በሳዑዲ ጎረምሶች የተደፈረና እንደ ኢትዮጵዉያን በየአደባባዩ የተገደለ የሌላ አገር ዜጋ የለም። ሳዑዲ አረቢያ ዉስጥ የሚገኙ የሌሎች አገሮች ኤምባሲዎች የዜጎቻቸዉ መብት በሳዑዲ መንግስትና ህዝብ ሲደፈር ለምን ብለዉ ይጠይቃሉ ወይም ለዜጎቻቸዉ ግዜያዊ መጠለያ፤ የህክምና እርዳታና የህግ ሽፋን ይሰጣሉ እንጂ ኤምባሲያቸዉ በራፍ ላይ “ዝግ ነዉ” የሚል ጽሁፍ አይለጥፉም።

የወያኔ ኤምባሲ ግን ከስረ መሠረቱ የተቋቋመዉ የወያኔን የራሱን እንጂ የኢትዮጵያን ህዝብ ጥቅም ለማስጠበቅ ስላልሆነ ይህንን የሌሎች አገሮች ኤምባሲዎች ለዜጎቻቸዉ የሚያደርጉትን ጥበቃና እንክብካቤ ለወገኖቹ ለማድረግ አልታደለም፤ ፍላጎቱም የለዉም።  ይህንን ቅሌትና ዉርደት ደግሞ ባለፉት ሁለትና ሦስት ሳምንታት በግልጽ ተመልክተናል። ጂዳና ሪያድ ዉስጥ በዜጎቻችን ላይ የሚደርሰዉን መከራና በደል ተቃዉመዉ ሠልፍ የወጡ ኢትዮጵያዉያን በሳዑዲ ፖሊሶች ታድነዉ እንደታሰሩ ሁሉ አዲስ አበባ ዉስጥም በወንድሞቻችንና እህቶቻች ላይ እንዴት እንዲህ አይነት በደል ይፈፀማል ብለዉ ሳዑዲ ኤምባሲ ፊት ለፊት ሠላማዊ ሠልፍ የወጡ ኢትዮጵያዉያን በአረመኔዎቹ የወያኔ ፖሊሶች ታድነዉ ታስረዋል፤ተደብድበዋል። አዎ! ኢትዮጵያዉያን ሳዑዲ ዉስጥም ኢትዮጵያ ዉስጥም ለምን የሳዑዲን መንግስት ተቃወማችሁ ተብለዉ በሁለቱም አገር ፖሊሶች እየታደኑ ታስረዋል ተደብድበዋል።

ከወያኔና ከጥቂት ሆድ አምላኪ ደጋፊዎቹ ዉጭ በአገር ዉስጥና በመላዉ ዓለም የሚገኘዉ ኢትዮጵያዊ በአንድ አላማ ዙሪያ የተሰባሰበበትና አንድ ሳምንት ሙሉ አንድ ቃል በአንድ ትንፋሽ የተነፈሰበት ግዜ ቢኖር ወርሃ ህዳር 2006 የመጀመረያዉ ነዉ ማለት ይቻላል። የአንድ አገር ህዝብ በአንድ አላማ ስር ሲሰባሰብና በአንድነት ሲቆም ከማንም ከምንም በላይ በዚህ አንድነት መጠቀምም መደሰትም ያለበት መንግስት ነዉ። ኢትዮጵያ ዉስጥ ያለዉ የወያኔ አገዛዝ ግን ዕቅዱና ስራዉ ሁሉ የኢትዮጵያን ህዝብ ማስጨነቅና ማበሳጨት ነዉ እንጂ የኢትዮጵያ ህዝብ በሚሰራዉ ስራ ተደስቶ አያዉቅም፤ ለወደፊትም የሚደሰት አይመስልም። ከሰሞኑ ሳዑዲ አረቢያ ዉስጥ በኢትዮጵያዉያን ወገኖቻችን ላይ የደረሰዉ ልክ የሌለዉ ስቃይና መከራ መላዉን የኢትዮጵያ ህዝብ ቀፎዉ እንደተነካ ንብ ከዳር ዳር ሲያስቆጣ ወያኔና ሞራለ ብልሹ ሹማምንቶቹ ግን ከዚህ ወገኖቻችንን በባዕድ አገር ለከፍተኛ ጥቃት ካጋለጠና ብሄራዊ ዉርደት ካከናነበን ክስተት ትርፍ ለማግኘት የፖለቲካ ቁማር እየተጫወቱ ነዉ። ኢትዮጵያዉያን ሳዑዲ ዉስጥ በአሰሪዎቻቸዉ፤ በመንደር ዉስጥ ጎረምሶችና በፖሊስ ከፍተኛ ድብደባ፤ እንግልትና ዉርደት ሲደርስባቸዉ ኤምባሲዉ በራፍ ላይ “ኤምባሲዉ ዝግ ነዉ” የሚል ጽሁፍ በመለጠፍ ይበላችሁ እያለ አፉን ዘግቶ የተመለከተዉ የወያኔ አገዛዝ ዛሬ የወገን አሳቢና ተቆርቋሪ ለመመሰል የጭቃ ዉስጥ እሾኩን ቴዎድሮስ አድሀኖምንና የአገዛዙን የዉሸትና የቅጥፈት ቃል አቀባይ ዲና ሙፍቲን በግምባር ቀደምትነት በማሰለፍ የፖለቲካዉን ገደል ቁልቁል ተያይዞታል።

ቴዎድሮስ አድሃኖም ቢከፋም ቢለማም የአገሪቱ የዉጭ ጉዳይ ሚኒስትር ነዉ፤ የዉጭ ጉዳይ ሚኒስትር የስራ ሀላፊነት ደግሞ አገሪቱንና ዜጎቿን ከዉጭ አገሮች ጋር በሚያገኛኙ ጉዳዮች ላይ ማተኮር ነዉ እንጂ በአገር ዉስጥ የሚሰራዉ ይህ ነዉ ተብሎ የሚነገር ስራም ሀላፊነትም የለዉም። አንዴ ወዳጅ አንዴ ጠላት እየመሰለ እንደ እስስት መልኩን የሚቀያይረዉ ቴዎድሮስ አድሀኖም ግን ሳዑዲ ዉስጥ ድረስልን ብለዉ ሲጣሩት ፊቱን ያዞረባቸዉ ኢትዮጵያዉያን አዲስ አበባ ሲመለሱ ያሉበት ቦታ ድረስ በመሄድ እንኳን ደህና መጣችሁ ለማለት ሲሞክር ይታያል።  ሳዑዲ አረቢያ ዉስጥ የሚገኙትን የኢትዮጵያ ኤምባሲና ቆንስላ ጽ/ቤቶች ቅርቅር አድርጎ ዘግቶ የወገን ያለህ ብለዉ የመጡትን ኢትዮጵያዉያን እንጃላችሁ ብሎ ፊቱን ያዞረባቸዉ የአዛኝ ቅቤ አንጓቹ ቴዎድሮስ አድሃኖም እነዚሁኑ እንደ ባዳ ፊቱን ያዞረባቸዉን ኢትዮጵያዉያን አገር ቤት ሲመጡ “እንኳን ደህና መጣችሁ” ማለቱ የገደለዉን ወታደር ለማከም ከሞከረዉ የናዚ ጀርመን ወታደር ተለይቶ የሚታይ አይደለም። ቴዎድሮስ አድሀኖም እንደ ፈረስ ገርተዉ ለዚህ ባደረሱት በነመለስ ዜናዊና ስብሐት ነጋ ጭቅላት ሳይሆን በራሱ ጭንቅላት የሚያስብ ሰዉ ቢሆን ኖሮ የሱ የስራ ድርሻና ሀላፊነት ዜጎቻችን አገር ቤት ከገቡ በኋላ ሳይሆን ሳዑዲ ዉስጥ እያሉ ነበር።

ዛሬ ቴዎድሮስ አድሃኖምም ሆነ ዘረኞቹ የወያኔ መሪዎች ከሳዑዲ በሚመለሱት ወገኖቻችን ዙሪያ የሚያደርጉት ልታይ ልታይ የፎቶ እሽቅድምድም ወገኖቻችንን ለመርዳት ሳይሆን ዘረኛ መሪያቸዉ መለስ ዜናዊ ሲሞት ሳያስቡት በድንገት ከእጃቸዉ የወጣዉን የጠቅላይ ሚኒስትርነት ቦታ መልሰዉ እጃቸዉ ለማስገባት ወይም በሚቀጥለዉ አመት በሚደረገዉና ወያኔ ከወያኔ ጋር በሚወዳደርበት ትርጉም የለሽ ምርጫ የፈረደበት ኃ/ማሪያም ደሳለኝን በቴዎድሮስ አድሃኖም ለመተካት ነዉ። አዎ! ለመተካት  . . . ለመተካካት። ወያኔ መተካካት እያለ አንዱን ጌኛ በሌላ ጌኛ በልቶ የጠገበዉን አህያ በተራበ አህያ መተካት ከጀመረ ዉሎ አድሯል። የአሁኑም ሩጫቸዉ ቢጭኑት አልሸከም ቢቀመጡበት አልመች ያላቸዉን ኃ/ማረሪያም ደሳለኝን የራሳችን ሰዉ ብለዉ በሚጠሩት በቴዎድሮስ አድሃኖም ለመተካት ነዉ (ኃይለማሪያምማ አሁንስ ቢሆን በቁሙ አልተተካም ብላችሁ ነዉ . . . ድፍን አበሻ ዉጭ አገርም አገር ዉስጥም ሲተራመስ ኃ/ማሪያም አንዲት ቃል አልተነፈሰምኮ) ።  ሳዑዲ ዉስጥ የሚገኙ ኢትዮጵያዉያን ወንድሞቻችን ፓስፖርታቸዉን ሲቀሙ፤ ሲደበደቡ፤ሲታሰሩና ሲገደሉ ቴዎድሮስ አድሀኖም የሰጠዉ ምላሽ ቢኖር  የኤምባሲዉንና የቆንስላ ጽ/ቤቶችን በር መዝጋት ነበር።  አዎ መዝጋት። ልክ ከ1997ቱ ምርጫ በኋላ ከመለስ ዜናዊና ከአግዓዚ ነብሰ ገዳዮች የጥይት እሩምታ ለማምለጥ ወደ ቤተክህነት ጽ/ቤት ግቢ ሸሽተዉ ለመግባት በሞከሩ ወጣቶችና ህፃናት ላይ አባ ጳዉሎስ በሩን እንደዘጉባቸዉ ዛሬም የአባ ጳዉሎስ ታናሽ ወንድም የሆነዉ ቴዎድሮስ አድሃኖም በባዕድ አገር ዉስጥ አድነን ብለዉ በተጠጉት ወገኖቻችን ላይ የኤምባሲን በር ቀርቅሮባቸዋል።

ለመሆኑ ቴዎድሮስ አድሃኖም በየአመቱ ከ40ሺ በላይ ኢትዮጵያዉያን ወጣቶች በለጋ ዕድሜያቸዉ ከወላጆቻቸዉ ተለይተዉና ትምህርታቸዉን ትተዉ ስራ ፍለጋ ወደ አረቡ አለም የሚጎርፉት እሱ ሊነግረን እንደሚፈልገዉ  በአትራፊ ደላላዎች ተታልለዉ ወይም የአረብ አገር ኑሮ ጥሟቸዉ ሳይሆን ወያኔ በሚከተለዉ የዘረኝነት ፖሊሲና የተበላሸ የኤኮኖሚ ስርዐት የተነሳ መሆኑን ያዉቅ ይሆን? በተለይ ወጣት ሴቶቻችን በአረቡ አለም የሚደርስባቸዉን ዉርደትና መከራ እያወቁ በነጋ በጠባ አረብ አገር የሚሄዱት አገራቸዉ ዉስጥ ሰርተዉ መኖር ስላልቻሉ ከወያኔ ጋር ከመኖር አረብ አገር ሄዶ መሰንበት ይሻላል ብለዉ ነዉ አይናቸዉ እያየ የሞት ወጥመድ ዉስጥ የሚገቡት። ወያኔ በእጥፍ ድርብ አሳደግኩት የሚለዉ የአለማችን ፈጣኑ ታዳጊ ኤኮኖሚ ለእነዚህ ዜጎች የስራ ዕድል ፈጥሮ ቢሆንና ዜጎች ስራ የሚያገኙት ችሎታቸዉ ብቻ እየታየ ቢሆን ኖሮ ይህ ዛሬ የምናየዉ ብሄራዊ ችግርና ዉርደት አይኖርም ነበር። ይሉኝታና እፍረት የሚባል ነገር አብሮት ያልተፈጠረዉ ቴዎድሮስ አድሃኖም የዜጎቻችንን ወደ አረብ አገር መጉረፍ በደላሎችም ሊያሳብብ ሞክሯል። አሱ ለሚከስሳቸዉ ደላሎች የስራና የንግድ ፈቃድ ሰጥቶ በዜጎች ንግድ እንዲከብሩ መንገዱን ያመቻቸዉና የከፈተዉ የራሱ የቴዎድሮስ ፓረቲ ነዉ፤ ብዙዎቹ አትራፊ ደላላዎችም የራሱ የቴዎድሮስ ጓደኞች ናቸዉ። የቴዎድሮስ አድሃኖም ጉድ ብዙ ነዉ፤ ተዘርዝሮ አያልቅም።

ኢትዮጵያዉያን ወገኖቻችን ሳዑዲ ዉስጥ ሲጋዙና ሲገደሉ ቁጥሩ ተገኗል እያለ በወገኖቻችን ላይ ያፌዝ የነበረዉ ቴዎድሮስ አድሃኖም ነበር፤ ኢትዮጵያዉያን ወገንና ረዳት አለን ብለዉ ወደ ኤምባሲዉ በብዛት ሲመጡ ኤምባሲዉና ቆስንላ ጽ/ቤቶች በራፍ ላይ “ዝግ ነዉ” የሚል ጽሁፍ ለጥፎ ወገኖቻችንን ለባዕዳን ጥቃት አሳልፎ የሰጠዉ ቴዎድሮስ አድሀኖም ነዉ፤የሳዑዲ መንግስት በአገሩ ዉስጥ ወንጀል ሲፈጸም ህጋዊ እርምጃ መዉስድ መብቱ ነዉ ብሎ የወገኖቻችንን መገደልና የሴቶች እህቶቻችንን መደፈር ህጋዊ ለማድረግ የሞከረዉም ቴዎድሮስ አድሃኖም ነዉ። የሚገርመዉ ይህ ወገኖቻችንን በባዕድ አገር “አይናችሁን ለአፈር” ብሎ በሩን የዘገባቸዉ ከሃዲ ሰዉ ነዉ ዛሬ የወገን አሳቢና ደራሽ መስሎ ቀልዱ እንዳማረለት የመድረክ ላይ ኮሜዲያን እዚህም እዚያም ሽርጉድ የሚለዉ። ሳዑዲ ዉስጥ በወገኖቻችን ላይ ለደረሰዉ ይህ ነዉ የማይባል ትልቅ በደልና ጥፋት የኢትዮጵያ ህዝብ በዋናነት ተጠያቂ ከሚያደርጋቸዉ የወያኔ ባለስልጣኖች ዉስጥ ቴዎድሮስ አድሃኖምና ተላላኪዉ ዲና ሙፍቲ የመጀመሪያዎቹ ናቸዉ።

ከሰሞኑ ፊቱን እያሳመረ በየደቂቃዉ ኢቲቪ ላይ መቅረብ የጀመረዉ ቴዎድሮስ አድሃኖም  “ሳዑዲ ዉስጥ ለደረሰዉ ጥፋት መንግስት ተመጣጣኝ እርምጃ ይወስዳል” እያለ ሲዘለብድ ተሰምቷል፤ የሱ ተላላኪ የሆነዉ ዲና ሙፍቲ ደግሞ “በዜጎች ላይ ምን ግዜም ድርድር የለም” ብሎ ሲናገር ተደምጧል። ይህንን በሁለት ባዶዎች የተነገረ ባዶ ንግግር ያዳመጠ የኢትዮጵያ ህዝብ ግን “ጽድቁ ቀርቶበኝ በወጉ በኮነንከኝ” እያለ የቴዎድሮስንና የዲና ሙፍቲን “ጅብ ከሄደ ዉሻ ጮኸ” ንግግር ሰምቶ እንዳልሰማ አልፎታል። የሚገርመዉ ይህ ወገኖቻችንን በክፉ ቀን ወግዱ ብሎ ፊቱን ያዞረባቸዉ ቴዎድሮስ አድሀኖም ነዉ ዛሬ የሳዑዲ መንግስት በራሱ ወጪ አዲስ አበባ የሚልካቸዉን ዜጎች ዘመድ መስሎ ለመጠየቅ የሚሄደዉ። ደግሞኮ እስከዛሬ ድረስ አዲሰ አበባ ገብተዋል የሚባሉት በጣት የሚቆጠሩ ሰዎችም ቢሆኑ በተለመደዉ የወያኔ የዘመድ አሰራር እየተመረጡ የመጡ እንጂ ዜግነታቸዉ፤ ዕድሜያቸዉና የጤንነት ሁኔታቸዉ እየታየ የተመረጡ ሰዎች አይደሉም። ባጠቃላይ የተጣለበትን አገራዊ አደራና የተሰጠዉን ህዝባዊ ሀላፊነት መወጣት የተሳነዉን ቴዎድሮስ አድሀኖምን በየሜድያዉና በተገኘዉ አጋጣሚ ሁሉ እያሽሞነሞኑ ለማቅረብ የሚደረገዉ ጥረት እንደ ህፃን ልጅ ሽንት መቀበያ የቆሸሸዉን የወያኔ ፊት በቆሻሻ ዉኃ ከማጠብ ተለይቶ የሚታይ አይደለም። ወያኔ ከአሳማ አሳማ እየመረጠ ለማሳመርና ለማሽቀርቀር የሚያደርገዉ ጥረት አሳማዉን ወደ ለመደዉ ወደ ጭቃዉ ዉስጥ ይበልጥ ይስበዋል እንጂ በፍጹም አያሳምረዉም፤ ምክንያቱም አሳማ አጌጥነዉ አላጌጥነዉ ምን ግዜም አሳማ ነዉ። የቴዎድሮስ አድሃኖም ነገርም እንደዚሁ ነዉ ፤ ወያኔ ያሻዉን ያክል ቢቀባዉና ቢያሳምረዉ ቴዎድሮስ አድሃኖም ወያኔነቱን አይለቅም! ወያኔ ደግሞ በልቶ የማይጠግብ ታጥቦ የማይነጻ አሳማ ነዉ።

ebini23@yahoo.com

↧
↧

መፍትሔው (አበራ ሽፈራው ከጀርመን)

$
0
0

አበራ ሽፈራው ከጀርመን

TPlFበተለይም ባለፉት 22 ዓመታት በሀገራችን ለተከናውኑት አበይት ችግሮች ሁላችንም እጆቻችንን ወደ ህወሓት እየቀሰርን ለችግሮቻችን መፍትሔ መስጠት አቅቶን ይባሱኑ ለከፍተኛ ስቃይና መከራ መዳረጋችንና፤ መፍትሔውን ከህወሓት እየጠበቅን ለችግራችን መባባስ አስተዋጽኦ በማድረጋችን ችግራችን እየተባባሰ ቀጥሏል። በምን መልኩ ነው አስተዋጽኦ አደረግነው?

በምን መልኩ አስተዋጽኦ አደረግን? ለምንል ደግሞ በተደጋጋሚ የህወሓትን ማንነት አይናችን እያየና እየተመለከት መስዋዕትነት ለመክፈል መወሰን ባለመቻላችንና የሀገራችንን እጣፋንታና የወደፊት እድላችንንም ጭምር በህወሓት እጅ አስቀምጠን አሁንም ለህወሓት ባርነት እራሳችንንና ሀገራችንን አሳልፈን መስጠታችን መቀጠሉ አስገራሚ ጉዳይ መሆኑና እኛም ለዚህ ውርደታችን መባባስ ለህወሓት ከፍተኛ እድል በመስጠታችንም ጭምር ነው።

ለችግራችን መፍትሔ ፈጣሪ ለመሆን እስካልቻልንና መፍትሔ የመፈለጉ ጉዳይ በራሱ በኢትዮጵያ ህዝብ እጅ እስካልገባ ድረስ አሁንም የህወሓት ጥቂት ጨቋኝ ቡድን የባርነት ቀንበር ተጭኖብን ለመኖር በመፍቀዳችን መፍትሔ አልባ ህዝቦች ሆነን ለመኖር መፍቀዳችንን ልንገነዘብ ይገባናል።

ባለፉት ዓመታት ህወሓት በሀገርቷና በህዝቧ ላይ መጠነ ሰፊ ግፍን ሲፈጽም ዝም ተብሎ ዛሬ እዚህ ደርሰናል። ሀገር እየተቆረሰ ለሌላ ሀገር ሲሰጥ፣ ህዝብ በጅምላ ሲገደል፣ ህዝብ እያፈናቀሉ ወደመጣህበት ዘር ሂድ ሲሉና የሰውን ልጅ ከደን ውድመት ጋር እያዛመዱ ሲሳለቁብን፣ በታጋይነት ሰበብ የአገሪቷን ጠቅላላ ወታደራዊ ሥልጣንን በቁጥጥር ውስጥ አስገብተው ጥቂቶች በህዝብ ሃብትና ንብረት ሲሳለቁ ፣ ጠቅላላውን የአገሪቷን የንግድ እንቅስቃሴ በመቆጣጠር የራሳቸውን የፓርቲ ንግድ ሲያስፋፉና ሌላውን የንግድ እንቅስቃሴ ሲያቀጭጩ እየተመለከትን፣ የአገሪቷ ህዝቦች በስደትና በመከራ ላይ ሆነው እነሱ የአገሪቷን መሬትች በመኖሪያ ቤት፣ በንግድ ቦታና በእርሻ ቦታነት እየተከፋፈሉ የራሳቸውን መስፋፋት ሲያጠናክሩ እየተመለከትን፣ በተለይም ላለፉት 22 ዓመታት የአገሪቷን የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤትን በሀገር ውስጥም ሆነ በውጭ ሀገር ያሉትን ጠቅልለው ይዘው የንግድና የራሳቸው የኑሮና የመስፋፋት ዓላማን ለማስፈጸም ከፍተኛ እድልን ፈጠረው ሲቀልዱብን አይናችን እያየ እየተመለከትን ለመሆኑ እኛ ማን ነን? ምንስ እንጠብቃለን?

ስለሆነም ህወሓት አሁን ካለበት ሁኔታ አንጻር በምን አይነት ሁኔታ እንዳለና ምን መፍትሔ መፍጠር እንደሚቻል ትንሽ ነገር ልበል።

የኢትዮጵያ ህዝብ ጠላት ህወሓት/ ኢህአዴግ አሁን ያለበት ሁኔታ በእኔ እይታ

ህወሓት ለአለፉት 22 ዓመታት ህዝቡን ሲረግጥ፣ ሲጨቁንና ሲከፋፍል የኖረ ከመሆኑ አንጻርና በህዝቡ ላይ ከመቼውም ጊዜያት ባልታየ ሁኔታ የኢትዮጵያ ህዝብን ለመከራ፣ለረሃብ፣ ለስደትና ለብዝበዛ ከበዳረጉም በላይ ጥቂቶች ባልተጠበቀ ሁኔታ በሃብት ጣራ የነኩበት ሀገር ከመሆኗ አንጻርና ከሌሎችም ተያያዝ ጉዳዮች ጋር ሲታይ ህወሓት ኢትዮጵያን ለመምራት ሃላፊነት በህዝቡ ሊሰጠው የማይችል መሆኑን ህዝቡና እራሱ ህወሓትና ባለሟሎቹ ጠንቅቀው ያውቃሉ፤ ይሁንና በጉልበትና በአንባገነነነት፣ እንዲሁም ህዝብን በማሸበር የመንግስትን ስልጣን ተቆጣጥረው ለመቀጠል ቆርጠዋል፡፡ የኢትዮጵያ ህዝብ አሁን እየደረሰበት ካለበት መከራ አኳያ ሲታይ ህወሓት ሁኔታዎች እንደከዚህ በፊቱ ሁሉም አልጋ ባልጋ ይሆኑለታል ማለት ግን አይደለም። ምክንያቱም ህወሓት እኩይ የሆነው ተግባሩ ሰፊ ጠላትን አፍርቶለታልና ነው። ስለሆነም ህወሓትን ከዚህ አንጻር ልንገመግመው እንችላለን።

1. ህወሓት በራሱ በህወሓት ውስጥ ሲታይ

በነገራችን ላይ ህወሓት ህዝባዊ መሰረት እንዳለው የሚነገረው ትክክለኛ አለመሆኑን የተለያዩ ማስረጃዎች ማሳየት ይቻላል። ህወሓት በመሰሪነትና በገዳይነት የሚታውቅ ድርጅት ከመሆኑ ጋር ተያይዞ በትግራይ ውስጥም ሆነ በራሱ በታጋዮች መካከልም ለዓመታት ታጋዮችን ጭምር በመግደል፣ በማሰቃየት፣ በማሰር፣ በማጥፋት እና መሰል የሽብር ተግባርን በመፍጠር ፍርሃትን በማንገሱ ፣እንዲፈራ በማድረግ በፍርሃት የተፈጠረ ድጋፍ እንጅ ሰው አምኖበት የደገፈው ድርጅት አልነበረም አሁንም አይደለምም። ህወሓት አሁንም በትግራይ ህዝብም ሆነ በሌሎች የኢትዮጵያ ህዝቦች ላይ እየፈጠረ ያለው አንባገነናዊ ሥርዓት በህዝቡ ፍላጎት ላይ የተመሰረተ ሳይሆን ህዝብን በመንግስታዊ ሽብርተነት በማስገደድ እንዲሰገድለት ማድረግ ትልቁ አላማ አድርጎ ያለ ድርጅት እንጂ በፍጹም በዲሞክራሲያዊ ግባቶች እንደማያምን የራሱ የፓርቲው አፈጣጠርና አመጣጥ በግልጽ ያሳየናል።

እነዚህ ሁኔታዎች ህወሓት በራሱ ፓርቲ ውስጥ ሰፊ የሆነን ጥላቻን ይዞና፤ ቂም በቀልን የያዞ መሆኑና ብዙዎቹ ሁኔታዎችንና ጊዜዎች እየተጠባበቁ ያሉ መሆናቸውንም ጭምር ሊገባን ይገባል። በተወሰነ አጋጣሚ ሁኔታዎች ቢለወጡ ብዙዎቹ ለመበቃቀል የሚፈላለጉ መሆናቸውን በግልጽ እናያለን፤ ከዚህም በላይ አሁንም ቢሆን በመሃከላቸው ትልልቅ ልዩነቶች ያሉባቸው ከመሆናቸው አንጻር ለአደጋ የተጋለጡም መሆናቸውንም በቀላሉ መረዳት እንችላለን።

2. ህወሓት በኢህአዴግ ውስጥ ካለው ቦታ አንጻር ሲታይ

  • ህወሓት ሌሎችን የኢህአዴግን ፓርቲዎች በማስፈራራትና የሚፈልገውን እየሾመባቸው ለመኖር የሚሻ መሆኑ
  • ሁሌም የበላይነትን ይዞ ለመቆየት ሲል ሌሎችን በማሰር፣ በመግደል፣ በማስፈራራትና የመብትና የዲሞክራሲያዊ መብት ጥያቄዎችን እንዳያነሱ በማድረግ ጥቂቶች በበላይነት እንዲቀጥሉ በማድረግ
  • ዋና ዋና የአገሪቷን ሥልጣኖች በሙሉ በራሱ ቁጥጥር ውስጥ ከማስገባቱ ጋር ተያይዞ በሌሎች ፓርቲዎች ውስጥ ተቀባይነቱ እየተሸረሸረ መሆኑና፤ በተለይም ከ1997 ምርጫ በኋላ አይን ያወጣ አንባገነንነቱን ይዞ መቀጠሉ ችግሩን በይበልጥ እየጎላ መምጣቱና በፓርቲዎቹ መካከል አለመተማመን እየተፈጠረ መምጣቱ
  • ጥቂቶች በመቀያየር እየተሽከረከሩ የሚያስተዳድሩት መሆኑና ለዘለቄታ የሚሆን መሰረት የሌለው መሆኑ
  • በራሱ አባላት ጭምር የተጠላ አንባገነን ፓርቲ መሆኑ

3. ህወሓት በኢትዮጵያ ህዝብ አንጻር

  • ጥቂቶች ይባስም ብለው በቤተሰብ ደረጃ የተሰባሰቡበት ቡድን መሆኑ መታወቁ
  • ኢትዮጵያን የማይወክል ቡድን መሆኑ መታወቁ
  • ጥቂቶች እስከ እድሜ ልካቸው ድረስ በዚህ ቡድን ውስጥ ተሸሽገው የኢትዮጵያ ህዝብ ደም እስከ ጡረታቸው ድረስ የሚፈልጉትን ለማደረግ እንዲችሉ የተዋቀረ የማፍያ ቡድን መሆኑ መታወቁ
  • ወታደራዊ ሃይሉን የሚያስተዳድሩ ኢትዮጵያውያንን የሚወክሉ ሳይሆኑ ጥቂቶች አንድን አካባቢ ብቻ የሚወክሉ ተሰባስበው አገሪቷንና ህዝቧን እያስፈራሩ ለመኖር የተዋቀሩ የማፍያ ቡድን አባላት መሆናቸው መታወቁ
  • በሙስና የተጨማለቁ መሆናቸው ህዝቡ ጠንቅቆ የሚያውቅ መሆኑ
  • ለህይማኖት ነጻነት ክብር የማይሰጥ መሆኑና የነጻነት አምልኮ መገደቡ መታወቁ
  • በአጠቃላይ በየትኛውም መለኪያ በኢትዮጵያ ህዝብ ዘንድ የተጠላ ቡድን መሆኑ

4. ህወሓት በመከላከያ፣ በፖሊስና በልዩ ልዩ ወታደራዊና የደህንነት መስሪያ ቤት ሲታይ

  • ኢትዮጵያ የመከላከያ ሰራዊቷና ሌሎች ወታደራዊ አደረጃጀቶቿ እጅግ በሚገርም መልኩ የአገሪቷ ሳይሆኑ የጥቂት ይልቁንም የአንድ አካባቢ ሰዎች ተሰባስበው የሚያስተዳድሩት መስሪያ ቤት ከመሆኑም በላይ በየትኛውም የአገሪቷ ታሪክ ታይቶ በማይታወቅ መልኩ አገሪቷ ለትልቅ የብዝበዛ መዋቅርነት እንዲያገለግል ተደርጎ የተደራጀ መሆኑ፤ ይህ ተቋም የአገሪቷ ተቋም ካለመሆኑ ጋር ተያይዞ ለወደፊቱም ቢሆን ለአገሪቷም ሆነ ለህዝቦቿ ነጻነት ትልቅ አደጋ መሆኑ
  • ብዙዎች የመከላከያ ሰራዊት አባላትም የአገሪቷ የመከላከያ አወቃቀር መስተካከል እንዳለበት በመጠየቅ ላይ መሆናቸው
  • ወታደሩ ለኢትዮጵያ ከማገልገል ይልቅ የእነዚህን ጥቂት ዘረኞች የብዝበዛ መዋቅር እያስጠበቁ መሆናቸውን እያወቁ መምጣታቸው።
  • በአጠቃላይ ወታደሩ በልዩ ልዩ ጭቆና ውስጥ ያለ መሆኑና ጥቂት ነገር የሚፈልግ መሆኑ

ከላይ እንደተመለከትነው ህወሓት በአጠቃላይ ባለፉት ዓመታት ህዝቡን ባስመረረ መልኩ መጠነ ሰፊ ግፍን በህዝቡ ላይ ፈጽሟል ከዚህ በላይ ምን እስከምንሆን እንደምንጠብቅ አላውቅምም ወይም አልገባኝም። አንድ ነገር ግን ይገባኛል፤ እሱም እያንዳንዳችን ለራሳችን፣ ለህዝባችንና፤ ለሀገራችን የሚጠቅመውን ባለማድረግ፣ በመፍራት፣ እራስን በመውደድ፣ ለግል ጥቅም በመራራጥ፣ በግድየለሽነት፣ ነግበዕኔ ባለማለት፣ ህወሓት ለአቀረበልን ልዩ ልዩ ጥቅማ ጥቅሞች እየተገዛን በመንበርከካችንና በጋራ ባለመታገላችን፣ ከጋራ ጠላታችን ከህወሓት ይልቅ ሌሎች ተቃዋሚዎችን ለመተቸት በመሽቀዳደማችንና በሌሎችም ምክንያቶች አሁን እየደረሰብን ላሉ ሀገራዊ ውርደቶች እንድንዳረግ ሆነናል። እነዚህን ነገሮች ለመቀየር እንችል ዘንድ ቆም ብለን ማሰብ መቻል ያለብን ጊዜ ግን አሁን መሆኑ ግልጽ እየሆነ መጥቶልናልና እስኪ እናስብ።

ህወሓት አሁን ለምናየው እኩይ ተግባሩ ታግሎ መጥቶ በምስጊን ህዝብ ደም በነጻነትና በእኩልነት ሰበብ ይህንን ተግባሩን ሲፈጽም እንዴት እኛ ለእውነተኛው እኩልነት መነሳትና የራሳችንን መብት ለማስጠበቅ እንዴት ያቅተናል? ለዚህስ መስዋዕት ለመሆን ለምን ተቸገርን? ማን መስዋዕት እንዲሆን እንጠብቃለን? ግንቦት ሰባት ታግሎ ነጻ እዲያወጣን፣ አርበኞች ነጻ እንዲያወጣን፣ ኦነግ ነጻ እንዲያወጣን ወይስ ሌሎች ነጻ እንዲያወጡን እንደኔ ድርጅት ነጻ አያወጣንም። መጀመሪያ እራሳችን በግል እራስን ነጻ ለማውጣት መቁረጣችንን ማረጋገጥ አለብን። ከዚያ በኋላ ነው ድርጅቶችን መፈለግ ያለብን፣ከዚያ በኋላ ነው በመረጥነው የትግል መንገድ ከጠላታችን ጋር መፋለም የምንችለው፣ በመጀመሪያ ነጻነት ያስፈልገናል ወይስ አያስፈልገንም የሚለው ጉዳይ ሊያግባባን ይገባል፤ ከዚያም ነጻነትን እንዴት እናገኛለን ካልን የመጀመርያው መልስ ድርጅትን መምረጥ ሳይሆን ለመታገልና መስዋዕትነት ለመክፈል መነሳትና መቁረጥ ያስፈልጋል፤ ከዚያም ከቆረጡ ታጋዮች ጋር መደራጀት ይጠብቅብናል። መስዋዕትነት ለመክፈል መቁረጥ ይኖርብናል ሲባል ግን መስዋዕትነት የህይወት መሰዋዕትነት ብቻ አይደለም የጊዜ፣ የገንዘብ፣የእውቀት ማካፈል፣ የመረጃ መስጠት፣ ሌሎችም እንዳሉ ማመንና በአንደኛው ወይም በሌላኛው የትግል መስክ ተሰማርቶና የትግሉ አካል በመሆን ወደትግሉ በመቀላቀል የጋራ ጠላታችንን ዓላማ መቀልበስ ጊዜ የሚሰጠው አይደለምና እሁን እናስብበት! ግዜው አሁን ነው! ያለንም መፍትሔም ይኸው ብቻ ነው።

እግዚአብሔር ኢትዮጵያን ይባርክ!

ሀገራዊ ውርደት ይብቃን!

አበራ ሽፈራው ከጀርመን
aberay12@googlemail.com  

↧

ሰበር አሳዛኝ ዜና

$
0
0

አሳዛኝ ዜና  ዛሬ ከጠዋት 12 ሠዐት በጊዮርጊስ ቤተክርሰትያን በር ላይ አንድ ሲሚንቶ የጫነ ሲኖ ትራክ ባደረሰው አደጋ የአራት (4) ሰው ህይወት ሲያልፍ እንዲሁም ለጊዜው ቁጥራቸው በትክክል ያልታወቀ ሰዎች ቆስለዋል፡ እንዲሁም በእሳት አደጋ በኩል ያለው የቤተክርስቲያኑ በር በአደጋው አንድ ጎኑ ፈርሶአል፡፡

 

1457

12
15 13 12
↧

ከሳኡዲአረቢያ በተመለሱ ዜጎች ላይ የሚፈፀመው በደል አገር ዉስጥም እንደቀጠለ መሆኑን የኢህአዴግ አባላት አጋለጹ

$
0
0

“ከተመላሾቹ መካከል የአክራሪ ፣የኦነግና የግንቦት 7 አባላቶች ስላሉ መዝግባችሁ በአይነ ቁራኛ ተከታተሉዋቸው’’

                                                 የመንግስት አመራር አካላት

ዋሽንግተን ዲሲ፤ ህዳር 19/2006 (ቢቢኤን) ፦ሳኡዲ አረቢያ ህጋዊ የመኖርያ ፍቃድ የሌላቸውን ዜጎች ማስወጣትዋን ተክትሎ በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውን ከእንግልትና ከስቃይ በሗላ ወደ አገራቸው ገብተዋል በማለት የኢትዮጵያ መንግስት ቢገልጽም ተመላሾቹ በገዛ አገራቸዉ ይሸማቀቁ ዘንድ በመንግስት ዘመቻ እንደተከፈተባቸዉም ለማወቅ ተችሏል።

በአማራ ክልል በኦሮሚያ ዞን ያሉ የመንግስት የአመራር አካላት ከተለያዩ ቀበሌዎች ለመጡ ካድሬዎች በሰጡት መመሪያ ከሳኡዲ አረቢያ የሚመጡ ዜጎችን በመመዝገብ ጥብቅ ክትትል እንዲደረግባቸዉና በአይነ-ቁራኛ እንዲመለከቷቸዉ ትዕዛዝ መተላለፉ ታዉቋል፡፡ከታማኝ የመንግስት ምንጮች ለማረጋገጥ እንደተቻለዉ ከተመላሶቹ መካካል የኦነግ የግንቦት 7 እና የአክራሪነት ዝንባሌ ያላቸዉ ኢትዮጵያዉያን ወደ ትዉልድ ቀዬአችዉ ይመለሳሉ በሚል ስጋት ነዉ-ክትትል እንዲደረግባቸዉ የታዘዘዉ።

መንግስት ባንድ በኩል ዜጎቹን ለማስመለስና በአገራቸው እንዲቋቋሙ ከፍተኛ ጥረት እያደረኩ ነው እያለ

ወደ አገራቸው በመመለስ ላይ ያሉ ዜጎች ተጠቃለዉ እንኳ ሳይገቡ ይህን መሰሉን ትእዛዝ በአመራር አካላት እንዲተላለፍ ማድረጉ መንግስት ለስልጣኑንጅ ለህዝቡ ደንታ እንደሌለው ያሳያል ሲሉ የገለጹም አሉ፡፡

በሰው አገር እንግልትና መከራ የደረሰባቸው ዜጎች ከደረሰባቸው የስነ-ልቦና ቀውስ ሳያገግሙ፣ቁስላቸው ሳይሽር እና የቤተሰብ ናፍቆትን ሳይወጡ ባይነ ቁራኛ ተከታተሉዋቸው አክራሪ ናቸው፣የኦነግ-ግንቦት 7 አባላት ናቸው በማለት መጠነ ሰፊ ዘመቻ ለመክፈትና ለማሸማቀቅ ከሚያደርገዉ የፕሮፓጋንዳ ስራ መንግስት ሊታቀብ ይገባል ሲሉ ቅሬታቸዉንም የሚያሰሙ ወገኖች አሉ።

sa12የዉጭ ጉዳይ ሚኒስቴሩ ዶክተር ቴዎድሮስ አድሃኖም ከሳኡዲ የሚገቡ ዜጎችን በአክብሮት ተቀበልን ዜጎቻችንን መልሶ ለማቋቋም ጥረታችን እንደቀጠለ ነዉ በማለት እጃቸዉን ለሳኡዲ ፖሊስ ያልሰጡ ኢትዮጵያዉያንን ወደ አገር እንዲመጡ መገፋፋታቸዉ መሬት ላይ ካለዉ ሁናቴ ጋር አለመመሳሰሉ አጠያያቂ ነዉ የሚሉም አሉ። ሚኒስቴሩ ይህንን አጋጣሚ በመጠቀም እራሳቸዉን በመላዉ አለም ከሚገኘዉ ኢትዮጵያዊ ጋር በፌስቡክና በትዊተር በማስተዋወቅና ገጽታቸዉን በማሳመር በቀጣዩ ምርጫ ጠቅላይ ሚኒስቴር የመሆን ህልማቸዉን ለማሳካት የምርጫ ቅስቀሳ (campaign) የጀመሩ ይመስላል በማለት አንዳንድ ተንታኞች ይገልጻሉ።

በሙስና የተራቆተ አመራርን የያዘዉ ኢህአዴግ፤ የዜጎች ሁለንተናዊ መብት ነፍጎ፣የ አገሪቱን ኢኮኖሚ አራቁቶ፣የፖለቲካ ተቀናቃኞችን አመናምኖ፣ በመቶሺዎች የሚቆጥሩ ዜጎችን ከአገር እንዲሰዱ አርጎ፣ኢትዮጵያዉያን በገዛ አገራቸዉ እንዲፈናቀሉ ሆኖ፣መሬት ለዉጪ ኢንቬስተሮች እየተሸጠ፤ ስርዓቱ ከህዝባዊ እንቢተኝነትና አመጽ ድኖ እንደተለምደዉ ተሸንፎ የሚያሸንፍበት ምርጫ ይከሰታል የሚለዉ በሒደት የሚታይ ቢሆንም፤ ከሳኡዲ ወደ ኢትዮጵያ የሚገቡ ጉዳተኞች ግንቦት7 ፣ኦነግ ወይም  አክራሪ ሊሆኑ ይችላሉ በሚል ግምት እንደየ-ዘራቸዉና እንደየ-ሐይማኖታቸዉ ክትትል እንዲደረግባቸዉ መደረጉን በሁናቴዉ ደስተኛ ያልሆኑ የኢህአዴግ አባልት ለቢቢኤን ገልጸዋል።

 

↧

የትግራይ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ (ትህዴን) “አንድነታችንና እኩልነታችን በኢህአዴግ መቃብር ላይ ይረጋገጣል”አለ

$
0
0

ከትግራይ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ (ትህዴን) የተሰጠ ወቅታዊ መግለጫ

አንድነታችንና እኩልነታችን በኢህአዴግ መቃብር ላይ ይረጋገጣል!

በህዝብ የተተፋው የኢህኣዴግ ስርአት ። የተለያየ ምክንያቶችን እየፈጠረ ህዝብን በማደናገር የስልጣን እድሜውን ለማራዘም ሲል እንደ አንድ አላማ ይዞ ሲንቀሳቀስ ቆይቷል፣ ይህንንም አላማው ከግቡ ለማድረስ እየተጠቀመባቸው ካሉ ዘዴዎች መካከል። በተለያዩ ስሞች የተሰየሙ በዓላትን በአዋጅ መልክ እያወጣ ። ህዝቡን የቤቱን ጉዳይ ትቶ በነዚህ በዓላት እንዲያተኩር ማድረግ ነው፣
የትግራይ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ (ትህዴን) “አንድነታችንና እኩልነታችን በኢህአዴግ መቃብር ላይ ይረጋገጣል” አለ
በዚህም በእያንዳዱ ወር በዓላት ተሰይመው እንዲቀመጡ ተደርጓል፣ እነዚህ በአዋጅ የተቀመጡ በዓላት ። ስርአቱ ለስልጣኑ አስጊ የሆነ ነገር ሲፈጠር የህዝቡን የአተኩሮ አቅጣጫን ለመቀየር አስቦ ከሚያቅዳቸው ሲሆን እንደ አብነት ለመጥቀስ ያክል የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት በስርአቱ ተግባሮች ተማሮ ስርአቱን በመቃወም እንዳይነሳሳና በመስጋት ለሰራዊቱ ተቆርቋሪ በመምሰል የካቲት 7 የሃገር መከላከያ ሰራዊት በዓል ቀን ሲል ሰየመ።
ስርአቱ በአገራችን ብሄር ብሄረሰቦች መሃል እየገባ እየፈጠረው ያለው የመበታተን እርምጃ። ህዝቡ ሊነቃበት በጀመረበት ግዜም ቢሆን። በማሃከላቸው ገብቶ ፍቅር፤ አንድነትና መቻቻልን እንዲሰፍን እንደሚፈልግ መስሎ በመቅረብ ህዳር 29 ቀን የብሄር ብሄረሰቦች ቀን ብሎ በመሰየም በየአመቱ እንዲከበር በማድረግ ለፕሮፖጋንዳ ፍጆታ በማሰብ ብቻ በሃገርና በህዝብ ሃብት ይጫወታል፣
በሌላ በኩል የአገራችን ከተሞች በመብራትና ንፁህ የመጠጥ ውሃ፤ የኑሮ ውድነትና ሌሎች መሰረተ ልማት እጥረት ባጋጠማቸው ግዜ። የከተማው ነዋሪ ህዝብ ከማንም ግዜ በላይ ተማሮ የስርአቱን እውነተኛ ገፅታና ምስል ሊረዳ በጀመረበት ግዜም። ህዳር 11 የከተሞች ቀን ብሎ በመሰየም። በብዙ ሚልዮን የሚገመት ገንዘብ እንዲወጣ በማድረግ። ዛሬም እንደተለመደው በባህርዳር ከተማ በዓሉን ለማክበር ሽሩጉድ ሲል ይታያል፣
ለመሆኑ በየትኞቹ ከተሞች ነው በዓላቱ እየተከበሩ ያሉት? እነዚህ ብንፁህ ውሃ እጥረት እየተሰቃዩና ለተለያዩ የውሃ ወለድ በሽታዎች ነዋሪዎቻቸውን በማጋለጥ ለሞት እየዳረጉ ያሉ ከተሞች? እነዛ በመብራት ሃይል እጥረት የምግብ ማብሰያ አጥተው በጨለማ ቤታቸው ሆነው በረሃብ አለንጋ እየተገረፉ በሚኖሩባቸው ከተሞች? ወይስ በመልካም አስተዳደር እጦትና በተወሰኑ ፈላጭ ቆራጭ ባለስልጣናት አበሳውን እያየ ያለው የከተማው ነዋሪ? በየትኞቹ የማይታወቁ የኢትዮጵያ ከተሞች ነው ይህንን የማታለያ በዓልና ዳንኬራ እየተደረገ የሰነበተው፣
ከኢህአዴግ የተማርናቸው ተግባራት ካሉ በእያንዳንዱ ወራት የተለያዩ በዓላት በማስቀመጥ ህዝባችንን ከስራ ውጭ ማድረግና በተለይም ለአያሌ ዓመታት ተምሮ ስራ አጥቶ እየተንከራተተ የሚውል የተማረ ወጣት ሃይል በስርአቱ ላይ ተቃውሞ እንዳያስነሳ በዓሎች በመጡበት ቁጥር ተደናግሮ እየጨፈረ እንዲውል ለማድረግ ሆን ተብሎ እየተካሄደ ያለ ነው፣
አሁንም ለመጪው ህዳር 29 ቀን የሚከበረው የአገራችን ብሄር ብሄረሰቦች ቀን የሶማሌ ክልል እንድያዘጋጅ እየተደረገ ያለበት ሁኔታ ነው ያለው፣ ለመሆኑ የኢትዮጵያ ሶማሌ ክልል ለምን ይሆን የተመረጠው? ተረኛ ስለሆነ ወይስ በዓሉን ለማዘጋጀት የሃላፊነት እጣ ስለደረሰው? እዚህ ላይ ልንረዳው የሚገባን ነጥብ አለ።
የኢህአዴግ ስርአት ሁሉንም የሚያደርገው እንቅስቃሴ ጥቅሙን ማእከል ያደረገ ስለሆነ። በያዝነው ዓመት የብሄር ብሄረሰቦች ቀን በኢትዮጵያ ሶማሌ ክልል እንዲደረግ መወሰኑ ዋነኛው ምክንያት። የኦጋዴን ህዝብ የስርአቱን ፀረ ህዝብ ተግባሮች ከመጠን በላይ ስላንገፈገፈውና ከዚህም በመነሳትም የተለያዩ አመፆችና ትግል በማድረግ ላይ በመሆኑ። በክልሉ ሰላም እንዳለና የክልሉ ህዝብ ከመንግስት ጎን እንደሆነ ለማስመሰል፤ በሚከበረው በዓል አሳብቦ የህዝቡን ቀልብ ለመሳብና እኩልነታቸው እንደተረጋገጠላቸው አስመስሎ። ለአገራችን ህዝብና ለአለም ማህበረሰብ ለማደናገር ያለመ እንደሆነ ሳይታለም የተፈታ የስርአቱ ተንኮል ነው።
ለማጠቃለል የኢህአዴግ ፈላጭ ቆራጭ ስርአት አገርንና ህዝብን ወደ ውድቀትና ኃላ ቀርነት ለማስገባት የተዘጋጀ ስርአት ስለሆነ። የአገር መከላከያ፤ የከተሞች፤ የብሄር ብሄረሰቦችና የባንዴራ ቀን ወ.ዘ.ተ እያለ በዓላት ቢደረድርም። ለህዝብና ለሃገር አስቦ ሳይሆን የጥቂት ግለሰቦች ጥቅም ለማረጋገጥና ስልጣኑን ላማራዘም አልሞ መሆኑን የሚታወቅ ነው፣
ስለዚህ ዛሬም ይሁን ነገ የኢህአዴግ ስርአት። በዓላት ለመፈብርክ ስለማይቸግረው ህዝባችን በስርአቱ እኩይ ተግባሮች ሳይደናገር። አንድነቱን ለማጠናከርና እኩልነቱን ለማረጋገጥ፤ ብሄሮችና ብሄረሰቦች በፍቅርና በአንድነት ተቃቅፎው እንዲኖሩ፤ኢትዮጵያዊነታችን እንዲከበር፤ በማንነታችን እንድንኮራና ችግራችን እንዲያበቃ ከተፈለገ። የስርኣቱ ግብኣተ መሬትን ማቀላጠፍ ይገባናል፣

↧
↧

በቅርቡ ሪያድ አሚራ ኑራ ዩኒቨርሲቲ በተነሳው ሁከት በአውቶብስ ተጨፍልቃ የሞተችው ነፍሰጡር ኢትዮጵያዊት ምስል ይፋ ሆነ (18+)

$
0
0

ኢትዮጵያን ሃገሬ ከጅዳ በዋዲ

በሳውዲ አረቢያ ከእሳት ወደ ረመጥ ያመራው የወገኖቻችን ህይወት አሰቃቂ እና ዘግናኝ በሆኑ አደጋዎች ታጅቦ ግፍ እና መከራው ቀጥሏል::

በቅርቡ ሪያድ አሚራ ኑራ ዩነቨርስቲ በተነሳው ሁከት በአውቶብስ ተጨፍልቃ የሞተችው ነፍሰጡር ኢትዮጵያዊት ምስል ይፋ ሆነ። ከአስራ ስምንት ዓመት በታች የሆኑ እንዲያዩት አይመከርም።
selamawi self
ኖቬብር 24 2013 ምሽት ሚን ዛህሚያ እይተባለ ከሚነገርለት ግዜያዊ መጠለያ «ወገን ማሰቃያ » ጣቢያ በ17 አውቶብስ ተጭነው ኤርፖርት እንወስዳችሃለን ተበልው ሪያድ ከተማ መለዝ እይተባለ ወደ ሚጠራ አሚራ ኑራ ዩንቨርስቲ እንዳቀኑ በሚገርላቸው እገኖቻችን እና በሳውዲ ፖሊሶች መሃከል በተነሳ ግጭት በአውቶብስ ተጨፍልቃ የሞተችው ነፍሰጡር እህታችን አሰቃቂ ሞት ይፋ ሆነ ።

በሪያድ የኢትዮጵያ ዲፕሎማቶች እና በኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ተወክለው ወደ ሳውዲ አረቢያ እንደግቡ የሚነገርላቸው የልዑካን ቡድን አባላቶች ይህን የወገኖቻችንን ዘግናኝ አሟሟት በዓይናቸው አይተውት እንደነብር የሚናገሩ ምንጮች ህይወቷ በአሰቃቂ ሁኔታ ላለፈቸው ነፍሰጡር ከማዘን ይልቅ ጉዳዩ ይፋ እንዳይወጣ አደጋው በተከሰተበት ወቅት ፎቶ ያነሱ ኢትዮጵያውያን ወገኖቻችንን የቅረጹትን ይህን ምስል ለማንም አሳልፈው እንዳይሰጡ ያስፈሯሯቸው ነደነበር ገልጸዋል።
selamawi self 2
በሳውድ አረኢያ ወገኖቻችን ላይ እይደረሰ ባለው አሰቃቂ ሁኔታ ኢትዮጵያውያን ከመቸውም ግዜ በላይ የከፋ ሁኔታ ውስጥ ስለሚገኙ ድምጻቸውንን ከፍ አድርገን መጮህ ይጠበቅብናል ።

↧

የሚኒሶታዉ ደብረ ሰላም መድሃኒዓለም ቤተ ክርስቲያን የወያኔ እጅ መንሻ አይሆንም

$
0
0

ከወንድሙ በላይነህ (ሚኒሶታ)

ሰሞኑን ከማቀርባት እህቴ ጋራ ጨዋታ ጀምረን ሳዉዲ አረቢ በወገኖቻችን ላይ እየደረሰ ሥላለዉ ስቃይና መከራ ስናወራ እህቴ ቆጣ ብላ፦ አይ እኛ ስለነሱ መከራ ልባችን እዬደማ ተጨናንቀናል፤ ሌሎች በቤተክርስቲያናችን ላይ ከሚዶልቱ ሰይጣኖች ጋር ዛሬ ተጋጭቸ መጣሁ አለችኝ፦ የምን ግጭት ስላት አባወች እኮ ቤተክርሲቲያን ወዳገርቤት ሲኖዶስ አስተዳደር ኢንዲገባ ቅስቀሳ አድርጊ ብለዉኝ በጣም ተናደድኩ ብላ ስትነግረኝ ከርሷ በባሰ ድንጋጤዉ እኔንም በቁሜ አፈዘዘኝ። ኢትዮጵያዉያን ባዓለማት ተበትነዉ እያለቀሱ፦ በአገራቸዉ መኖሪያ አተዉ በሰዉ አገር እየተደበደቡ፦ እዬተደፈሩ፦ እየሞቱ እንዴት ዛሬ ወደወያኔ ለመግባት ቅስቀሳ አካህጅ ይሉኛል ብላ አለቀሰች። ጀሮ ከተማ ነዉ ሁሉ ይሰማበታል፦ በእርግጥም ከሃያ ሶስት የግፍ ስርዓት ዓመታት በሗላ ይህንን መስማት ያስደነግጣል፦ እንዲያዉም በዉጭ ያለን ኢትዮጵያዉያን ሁሉ በሳዉዲ አረቢያ እዬተጎዱ ላሉ ወገኖቻችን ተባብረን በአንድ ላይ በምናለቅስበት ሰዓት ይህን አፍራሽ ስራ ከጀመሩ መድሃኒዓለም ስራዉን ይሰራል አልኳት እና ጨዋታየን አቋረጥኩ።
deb
ደሙ የዋጀበትን መስቀል ተሸክመዉ ግን የዕምነት ይህይዎታቸዉ በመዋዕለ ንዋይ ህሊናቸዉ የተሰዎረ የወያኔ ምልምል ቄሶችና ዘማሪዎች ለጥቅማቸዉና ለወደፊት ሹመታቸዉ የባዘኑ ተስፈኞች ቤተ ክርስቲያናችን ለወያነዉ ፓትራሪክ ለማስረከብ ሃያ አራት ሰዓት በሴራ ተጠምደዉ ደፋ ቀና በማለት ላይ ይገኛሉ። እኩይ ስራቸዉን ተግባራዊ ለማድረግም በመድሃኒአለም በራፍ የታየ ምዕመናንን ሁሉ በጌቤታቸዉ እዬጋበዙ ወደ አገርቤቱ ሲነዶስ ለማስገባት ቀስቅሱ እያሉ መሃላ የሚያስገቡት ቁጥር ጥቂት አይደሉም። በወያኔ ዉስጣዊ ሎሌነት ታማኝ የሁኑት ቀንደኛወች ከአሁኑ ጀምሮ የሚቸራቸዉ (የሚሰጣቸዉ),ሹመት ምን እንደሆነ፦ በኢትዮጵያ ዉስጥ የከፈቱት ቢዝነስ ለነሱ ብቻ ሳይሆን ለአገሪቱ ተስፋ እንደሚሆን ተረጋግጦላቸዉ፦ ተማሪ የሆኑ ዘማሪያን ም ለ SCHOLAR እንደሚከፈላቸዉ ቃል እዬተገባ መሆኑ አንዳዶችን ነገሩ አስደንግጧቸዉ ለመቃወም በመነሳሳት ላይ ናቸዉ።

የሚገርመዉ ነገር አብዛኛወቹ በቤተ ክርስቲያኑ ምስረታና ግንባታ ያልነበሩ፦ እዳ ከተከፈለ ለስዉር ዓላማ በወያኔ የዘር መስመር አምነዉ ለመጥፎ ተግባር የተሰገሰጉ፤ ነገር ግን እራሳቸዉን መስራች ነን ብለዉ የመዘገቡ፦ በድምጽ ለማሸነፍ የአብዛኛ አባላት ድጋፍ ለማግኘት በየሰፈሩ እየተዘዋወሩ መልካም ዘመድ መስለዉ ለማሳመን የቆጡን የባጡን እያሉ ነዉ። ለመሆኑ ወያኔ ምን አዲስ ነገር ይዟል ብለዉ ሊያሳምኑን ፈለጉ? የህዝቦቻችን ድምጽ ለሃያ ሶስት ዓመታት በወያኔ ሙሉ በሙሉ ታፍኖ፤ ሃይማኖታችን በዘር ስርዓት ተቦርቡሩ፤ በወያኔ የበላይነት በየአድባራቱ ተመዝብሮl፦ የዕምነት ነጻነት ተነፍጎ። አሁን በያዝነዉ ወር እንkኳን በሳዉዲ አረቢያ ጥቃት ለደረሰባቸዉ ኢትዮጵያዊያን በአዲሳበባ ድምጻቸዉን እንዳያሰሙ ወገኖቻችን ተከልክለዉ መንግስት አጣን እያሉ ከሰባት ወራት ጩኸት በሗላ ለሞት ሲዳረጉ፦ አገራዊ ዉርደት ሲደርስብን እንዴትስ የወያኔ አጋርነት አሁን ይሞከራል? ወይስ አባ ማትያስ የወያኔ የዘር ምልምል ካድሬ ጳጳስ አደሉም ብለዉ ለማሳመን እየተጃጃሉ ነዉ። እኛማ አዉቀናል……:አያጅቦ ጅቦ ሳታመካኝ ብላኝ።

በሚኒሶታ ኢትዮጵያዉያን በህይወት እያለን ደብረ ሰላም መድሃኒአልምን ወያኔ አይረከበዉም። አወ ሰሞኑን እኛን እዉነተኛ አማኞችን ለማዋረድና በወያኔ ቃል የተገባዉን ለማሳካት፤ ግድያ ለመጣል፤ የነጻነቱን ትግል እንደበረዶ ለማቀዝቀዝ፦ በአህዝበ ክርስቲያን ላይ የመርዝ ሴራ የምትረጩ ሁሉ መድሃኒአለም በሩን ዘግቷል። ከወደቃችሁ በሗላ ወያኔ እንደማያነሳችሁ ካሁኑ እወቁት፤የቆጡን አወርድ ብላ የብብቷን ጣለች እንዳይሆንባችሁ ወዮላችሁ። ይልቅስ እናተዉ የሃጣን ሎሌ ሁናችሁ ንጹ ጻድቃንን ግራ አታጋቡ፤ሰላም አታችሁ ህዝበ ክርስቲያን አታስቆጡ። እዉነት ልበላችሁ እሚመቻችሁ ከሆነ ከዚህ አሜሪካ ካሉ የወያኔ ቤተክርስቲያናት መጀመሪ ጠቅላችሁ ግቡና የወያኔን አስተዳደር ሞክሩት በቤተ ክርስቲያን እንኳ ምርጫ ማካሄድም አትችሉም። እኛ የምንለዉ መድሃኒአለምን ተዉት ወይም ሃብታችሁን ይዛችሁ ልቀቁት። ከእንግዲህ ይህ የተቀደሰ ቦታ የንግድም ሆነ የስልጣን ቦታም አይሆንም። እናንተ እጃችሁን ስጡ የዕምነት ቦታችን ግን እጅ መንሻ ለማድረግ ፍጹም አትሞክሩ። ህዝበ ክርስቲያን ሆይ የእግዚአብሔር ቤትህን ጠብቅ።

ከወንድሙ በላይነህ

ወስብሃት ለእግዚአብሔር

↧

ከቤሩት የተሰማ አሰቃቂ መረጃ (ይህን ቪድዮ ከ18 ዓመት በታች የሆኑ እንዲያዩት አይመከርም)

$
0
0

ወደ ዘ-ሐበሻ ዝግጅት ክፍል በፌስቡክ የግል መልዕክት አንድ እህት ብታነጋግሩኝ አሳዛኝና ማንም ያልዘገበው መረጃ ቤሩት ውስጥ የተፈጸመ አቀብላችኋለሁ አለችን። ፈቃዳችንን ገልጸን ስልኳን ተቀብለን ወደ ቤሩት ደወልንላት። አነጋግርናት። ሌሎችንም እንዲሁ አንጋገርን። ከዚያም የሚከተለው አሳዛኝ መረጃ እንዲህ ተቀናበረ።

↧

በቃን ሊባል የሚገባው ሥርዓት (ዮናስ አዲሱ ቱፋ)

$
0
0

ዮናስ አዲሱ ቱፋ / ከጀርመን

Bekaበየትኛውም ታሪካችን በህወሓት/ኢህአዴግ ዘመን ኢትዮጵያውያን እንደተዋረድን መቼም ተዋርደን አናውቅም ።  ሊያውም በዚህ ዓለም በሰለጠነችበት ዘመን የአገሬ ህዝቦች ለስደት የተዳረግንበት፣ በልዩ ልዩ አገራት ለችግር የተዳረግንበት፣ ጥቂቶች አይን ባወጣ ብዝበዛ ውስጥ የተሳተፉበት፣ የህዝቦች የመሬት ባለቤትነት ተነጥቆ የአገሪቷ መሬትና የተፈጥሮ ኋብቶች በጥቂቶች በቁጥጥር ስር የሆነበት ዘመን ፣ የተወሰኑ ኋይሎች አገሪቷን በቁጥጥር ስር አስገብተው ህዝቡን በሚፈልጉት መንገድ የሚመሩበት ፣ ህዝቡና አገሪቷ በግዳጅ የምትመራበት ዘመን ሊያውም በሰለጠነ ዘመን፣ አገራችንና ህዝቦቿ በእፍረት ውስጥ የወደቅንበት ዘመን፣ የህዝባችን መከራ ከሃገራችን አልፎ በውጭው አገራት በመከራ ላይ ያለንበት ዘመን ፡፡

ይበልጥኑም የአገራችን ወጣቶችና ሴቶች በአገሪቷ ውስጥ የስራ እድል የሚሰጠው ለኢህአዲግ አባላትና ደጋፊውች ብቻ እንደሆነ   አውቀው የሰው አገርን እንደተሻለ የስራ እድል ስፍራ የመረጡ እህቶቻችንና ወንድሞቻችን በየአረብ አገራት ለዓመታት ሊያውም በከፍተኛ ችግርና መከራ ውስጥ ሆነው፣ ያለባቸውን ጭቆናንና መከራ ተቋቁመው በኖሩና በአገር ቤት ለሚገኙ ዘመዶቻቸው በተለይም በድህነት ያሳደጓቸውን  አባትና እናቶቻቸውን ለመደጎም ቁምስቅላቸውን እየዩ በሚኖሩባት ሳውዲአረቢያ ይባስ ብሎ ወገንና አገር እንደሌላቸው ፤ ይልቁንም ሊከላከልላቸው የሚችል መንግስት እንደሌላቸው የተረዱት ሳውዲ አረቢያዎች፤ በሌሎች  አገራት ዜጎች ላይ ባልፈጸሙት መልኩ ኢትዮጵያውያኑን ዓለም ሁሉ እያየ ሲግድሏቸው፣ ሲገርፏቸው፣ ሲደፍሯቸው፣ እየገደሉ ስጋቸውን ሲቆራርሱና እንደውሻ በመንገድ ላይ ሲታዩ ማየት ምን ያህል ያደማል፣ ያቆስላል፣ ያማል፣ ያስለቅሳል።

የሳውዲ አረቢያው በዚህ መልኩ ታየ እንጂ በሌሎችም የአረቡ ዓለም በኢትዮጵያውያን ላይ እየደረሰ ያለው ችግርና መከራ ምን ያህል አስቸጋሪና የከፋ መሆኑን በቀላሉ መገመት ይቻላል። በአረቡ አለም የታየው ስቃይ ምን አልባትም ኢትዮጵያውያን በአገራችንም ከምናየው መከራና ስቃይ በምንም መልኩ እንደማይተናነስ ከማንም  የተሰወረ አይደለም። በአረቡ አለም የተፈጸመው በባዕዳን የተፈጸመ ከመሆኑ ውጭ በመንገድ ላይ ተገደሉ አገር ቤትም ውስጥ ግድያ አለ፣ እስራትና ድብደባም በአገር ቤትም አለ፣ ችግርና ድህነት በአገር ቤት በዝቶ አይደለም እንዴ እህቶቻችን ለመሰደድ የተዳረጉት ፣ ሳዊዲአረቢያ ሁሉም  በህግ ወጥ መንገድ በሌላ አገር ዞረው ወጡ እንዴ? አይመስለኝም! ብዙዎች የህወሃት ባለማዋሎች  በደላላነት በተሰማሩበት የሰዎች  ማዟዟር አማካኝነት ይህ እንደተከናወነ እየታወቀ  እንዳላወቁ እየሆኑ ህወሃቶች በህዝቡ ላይ ሲያላግጡ ያሳዝናል። ለመሆኑ ከአገር ተደብቆ የወጣው ምን ያህሉ ነው? አብዛኛው ወጣት መሆኑና ይልቁንም በዚሁ በአገራችን ዘረኛ ቡድን አመራር ዘመን  የተወለዱና ያደጉ መሆናቸውን ማንም ምንም መረጃ ሳያገላብጥ በመገናኛ ብዙሃን ላይ ያሉትን ፎትግራፎች አይቶ በቀላሉ መገመት ይችላል።

ዛሬ አገራችን ለራሳቸው ጥቅም በተደራጁ ሃይሎች እየተመራች መሆኑ፣ ለአገር ሳይሆን ለቡድናዊ ጥቅሞቻቸው ቆርጠው በተነሱ፣ ለአገሪቷ ህዝቦችና ለአገሪቷ ምንም የማይቆረቆሩ ተሰብስበው አገሪቷን የሚመሩ በመሆኑ ፤ ምንም የህዝብ ውክልና ሳይኖራቸው በግድና ህዝብን በማስገደድ ለሁሌም አገሪቷን ለመበዝበዝ በቆረጡ ኋይሎች እጅ ወድቃ ያለች አገር በመሆኗ ፤ የተፈጠሩ ችግሮች እንጂ በህዝብና በመንግስት መካከል ልዩነቶች ባይኖሩና ኢትዮጵያውያን ለአገራቸው በጋራ ሰርተን መኖር አቅቶን አይደለም፣ ማደግም አቅቶን አይደለም፣ ተሳስበን ለሃገራችን መስራትም አቅቶንም አይደለም ፣ 22 ዓመታት አሁን ካለንበት ውድቀት ለመዳንበቂ ጊዜ ሳይሆን ቀርቶም አይደለም።

በኢትዮጵያውያን  ስም ከውጭ አገራት  በብድር፣ በእርዳታና በንግድ የተሰበሰቡ ገንዘቦችን በውጭ ባንኮች እያሸሹ የሚያስቀምጡት እነማን ሆኑና ህወሓቶች አይደሉምን? በአገሪቷ ሃብት ላይ የብዝበዛ ስራን የሚፈጽም ማን ሆነና ህወሓቶች አይደሉምን ? ለዚህስ የህዝብ ድህነት ላይ መውደቅና ለችግር መዳረግ ምክንያቱ ማን ሆነና ህወሓቶች አይደሉምን ? ዛሬ ሀብታሞቹና በአገሪቷ ውስጥ እንደፈለጉ በአገሪቷ ሃብት የሚባልጉት እነማን ሆኑና ህወሓቶች አይደሉምን ? ዛሬ የአገሪቷ ህዝብ መከራ የሚያየው በማን ሆነና ነው ዛሬ ህወሃት/ኢህአዲግ አሳቢ ሆኖ ለመታየት የሚፈልገው ?

የችግሮቻችን ምክንያቶች የህዝባችን ስንፍና፣ አልሰራ ባይነት እና ተመሳሳይ ጉዳዮች ሳይሆኑ ህወሃት የፈጠረው የማህበራዊ፣ የፖለቲካና የኢኮኖሚ ምስቅልቅል እንጂ ህዝቡ በራሱ ላይ የፈጠረው ችግር እንዳልሆነ ማንንም ለማስረዳት መሞከር አያስፈልግም። ሁሉም ኢትዮጵያዊ ሁሉ የችግሩ ምክንያትንም ሆነ የአገሪቷንና የህዝቧን መከራ ምክንያቶች ህወሃቶች እንደሆኑ በግልጽ ያውቃል  ። ይህንንም አፍረት ለመቋቋም ህዝቡ የሚችለውን ለማድረግ የቆረጠበት ሰዓት ነው።

እንግዲህ ህወሃቶች የአገሪቷና የህዝቧ እፍረቶች ስፍራችሁን አዘጋጅታችኋል፣ የምትፈልጉትን በዝብዛችኋል፣ አይን ያወጧ ዝርፊያን ፈጽማችኋል፣ ዘረኝነትን አንግሳችሁ ህዝቡን በመለያየት ለጋራ አላማ እንዳይሰራ አድርጋችኋል፣ ለእናንተ የብዝበዛ ዘመናችሁን ለማርዘም ጠቅሟችኋል ለህዝቡና ለአገሪቷ ግን ትልቅ ፈተናና መከራ ሆናችኋላና ይበቃችኋል ።  እናንተ የማትሸከሙትን ሁሉ አሸክማችሁ አሰቃይታችሁታል፣ በእናንተና በልጆቻችሁ ወይም በቤተሰቦቻችሁ ላይ ሊደርስ የማትፈልጉትን ፈጽማችሁበታል። አሁን ለራሳችሁ ስትሉ የምታስቡበት መስቀለኛ መንገድ ላይ ትገኛላችሁ።

ይህ ካልሆነ ግን ህዝቡ ብዙ ታግሷል፤ አሁን ግን የእፍረታችን ምክንያቶች የሆናችሁ ህወሃቶች ካልሆነ ግን ይህ የፈጸማችሁትን ግፍ ለፍርድ የሚያቀርብን ትግል እያፋጠናችሁ እንደሆነ ልመክራችሁ እፈልጋለሁ። አገራችን የናንተ ብቻ ሳትሆን የሁላችንም ናት። ወደዳችሁም  ጠላችሁም የአገሪቷ መጻኢ ፋንታን የመወሰን መብት የአገሪቷ ህዝብ እንጂ የጥቂት በዝባዥ ህወሃቶች እንዳልሆነ ሊታወቅ ይገባል።

የአገሬ ህዝቦች ዛሬ የችግራችንን ጥልቀት ከዚህ በኋላ በጽሁፍ በማስረዳት መሞከር የሚያስፈልግበት ጊዜ ላይ አይደለንም  ማንም ኢትዮጵያዊ ሁሉ የህወሓት/ኢህአዴግ ችግር እቤቱ ያልገባ የለም፣ በህወሃት ያልተገደለ የለም፣ በህወሃት/ኢህአዴግ ክብሩ ያልተነካ የለም፣ በህወሃት/ኢህአዴግ ያልተሰደደ የለም፣ በህወሓት/ኢህአዴግ ቤት ንብረቱ ያልተነጠቀ የለም፣  በህወሓት/ኢህአዴግ ያላለቀሰ የለም ዛሬ ግን በአንድ ጉዳይ ላይ ልንስማማ ይገባናል። ይህም የዚህ ሁሉ ችግር ምክንያትና የመከራችን ሁሉ፣ የአፍረታችንም ሁሉ ምክንያት በሆነው በህወሓት/ኢህአዴግ መቃብ ላይ የተስፋችንን ችቦ ማውለብለብ ይገባል። ለዚህም የኢትዮጵያ ህዝብ ሁሉ ለትግል ሊቆርጥ ይገባል። በህወሓት/ኢህአዴግ መቃብር ላይ የተስፋችንን ችቦ እናቀጣጥል! በዚህም የአገራችን ህዝቦች መከራ ያብቃ!   አት ባለሓት ሕሕሕ

 

ድል ለኢትዮጵያ ህዝቦች !

↧
↧

ማን ነው የተዋረደው? (ይሄይስ አእምሮ)

$
0
0

ይሄይስ አእምሮ

ከጥቂት ሣምንታት ወዲህ በተለይ የኢትዮጵያን የወያኔ መንግሥት በሚቃወሙ የሚዲያ ማዕከላት ዘንድ ዋና መነጋገሪያ ሆኖ የሚገኘው በሳዑዲ የኢትዮጵያውያን መንገላታትና መሰቃየት እንዲሁም ከኢሰብኣዊነትም በወረደ ሁኔታ በግፍ መጨፍጨፍ ነው፡፡ ዜጎቻችን በአካፑልኮ ቤይ የመዝናኛ ሥፍራ ሲንሸራሸሩ ከርመው የመጡ ይመስል ይህ ምስል በኢትዮጵያው የወያኔ ሚዲያ በአስደሳች መልክ እየቀረበ ቢሆንም ትክክለኛውን መረጃ ከአማራጭ የዜና ምንጮች እንደወረደ እንደምንከታተለው ከሆነ ግን ከሀገርና ከሕዝብ ኅልውና አኳያ ነገሩ እጅግ አሳሳቢ ነው፡፡ ከአንድ ጨለማ ውስጥ ብርሃን እንደሚጸነስ ሁሉ ከዚህ አስከፊ ገጠመኝ ውስጥ የፈነጠቀው የሕዝብ አንድነት ግን በሌላ ወገን ተስፋችን እንዲያንሠራራ አድርጓል፡፡ ፈረንጆቹ “blessing in disguise” ወይም “mixed blessing” እንደሚሉት ይህ መጥፎ አጋጣሚ ሊረሳ የተቃረበውን የሕዝብ አንድነት በማደስ በመላው ዓለም የተበተነው ኢትዮጵያዊ በአንድነት ቆሞ ድምፁን እንዲያሰማና ለጋራ ኅለውናው እንዲያለቅስ አስችሎታል፡፡ በተመሳሳይም የሕዝቡ ስሜትና እውነተኛ ፍላጎት በየስብሰባዎቹና ሰላማዊ ሰልፎቹ ሲንጸባረቅ እንደተመለከትነው ወያኔን ከመሰሉ በርካታ ከፋፋይ የዘር ፖለቲከኞችና የሃይማኖት ቡድኖች ሸረኛ ሤራ ባፈነገጠ መልኩ በአንድ ሉዓላዊ መንግሥትና በአንድ ሰንደቅ ዓላማ ሥር የመኖር የቆዬ ኢትዮጵያዊ አብሮነቱን የታዘብንበት ሁኔታ ተፈጥሯል፡፡ በሌላ አቅጣጫ ደግሞ በዚህ ስቃይ ለማትረፍ የሚፈልጉ በተለይም ወያኔዎችና መሰል ልበ ደንዳናዎች ለምርጫ ዝግጅት በፕሮፓጋንዳነት ሲጠቀሙበት፣ ለገቢ ማግበስበሻም ከማዋል እንደማይመለሱ እየተነገረ ነው፡፡

ከጓደኞች ጋር ስንወያይ አንዳንዶቻችን ይህ ነገር በኢትዮጵያና በኢትዮጵያውያን ላይ ብቻ የተነጣጠረ ሣይሆን በአጠቃላይ በሰው ልጅ ኅልውና ላይ የተቃጣ ታላቅ የክፍለ ዘመኑ ወንጀል መሆኑን ተገንዝበናል፡፡ ስለዚህ ማፈር ያለበት ነጭ ጥቁር ሳይል የሰው ልጅ በአጠቃላይ እንጂ ኢትዮጵያውያን ብቻ አይደሉም ወደሚለው እሳቤ አዘንብለናል፡፡ አንድ የዓለም ዜጋ በመጥቆር በመንጣቱ ወይም በመክበር በመደኽየቱ፣ በዚህ ወይ በዚያ ዘውግ አባልነቱ፣ በዚያ ወይ በዚህ ቋንቋ ተናጋሪነቱ፣ ወይም በመስለምና ባለመስለሙ፣ በክርስትና እምነትም በመጠመቁ ወይ ባለመጠመቁ ሣይሆን በኢትዮጵያዊነቱ ብቻ እንዲህ ዓይነት ዘግናኝ ግፍ የሚደርስበት ከሆነ ነግ ከነግ ወዲያ ታሪክ ሲለወጥ ይህ ዓይነቱ ውርጅብኝ በማንም ሌላ ወገን ላይ እንደማይደርስ ማንም ዋስትና ሊሰጥ አይችልም፡፡ ዛሬ በኢትዮጵያውያን ላይ የደረሰው ዕልቂት በሁለተኛው የዓለም ጦርነት ወቅት በአይሁዶች ላይ ከደረሰው ቢበልጥ እንጂ አይተናነስም፤ አሁን በኢትዮጵያውያን ላይ በሀገራቸው ውስጥም ሆነ ከሀገራቸው ውጭ እየደረሰባቸው የሚገኘው ዕልቂት ሩዋንዳና ዩጎዝላቪያ ወይም ኢራቅና አርመን ውስጥ ከደረሰው ጭፍጨፋ ቢብስ እንጂ አያንስም፡፡ መነሻ ምክንያታቸው የሚለያዩ ግን ይበልጡን ከኢኮኖሚ ጥቅምና ከዓላማ ቁርኝት ጋር የሚያያዙ የሰው ዘር ፍጅቶች በየዘመናቱ በብዙ ሀገራት ተፈጽመዋል፤ አሁንም ድረስ በመፈጸም ላይ ናቸው፡፡ ነገር ግን ግንዛቤ ያላገኘው ነገር በአንዱ ላይ የሚፈጸመው ነገር በለሌላው ላይ እንደተፈጸመ ያለመቁጠር ነው፡፡ ይህ ትልቅ ዓለም አቀፍ ችግር ነው፡፡ በአንድ የየትኛውም ሀገር ዜጋ ላይ የሚደርስ ችግር በማንኛውም የሰው ልጅ ላይ እንደደረስ ችግር ካልተቆጠረ በሰው ልጆች አጠቃላይ አስተሳሰብ ላይ የተዛባ ነገር አለ ማለት ነው፡፡ ይህ የተቃወሰ አስተሳሰብና አመለካከት መፍትሔ ካላገኘ የሰው ልጅ በውድቀት መንገድ እንደነጎደ ይቀጥላል ምፅዓቱንም ያቃርባል እንጂ ዓለማችን ወደተሻለ ኅሊናዊና ቁሣዊ የዕድገት ጫፍ አትደርስም፡፡

ዛሬ በኢትዮጵያ ላይ እየደረሰ ያለው መከራና ውርደት ወቅቱን ጠብቆ ነገ በሌላ ሕዝብና መንግሥት ላይ ይደርሳል – እንደእስካሁኑ ሁሉ፡፡ ይህ አነጋገር የትንቢት ጉዳይ ሣይሆን ማንም አእምሮ አለኝ የሚል የዓለም ዜጋ ሁሉ ሊረዳው የሚችል ነባራዊ እውነታና የማይሸሹት ወረፋ ነው – ወረፋ እስኪደርስ ያለው የጊዜ እርዝማኔ እያነሆለላቸው ብዙዎች ይሞኛሉ፡፡ ያዋጣ የነበረው አካሄድ ግን በምንም ዓይነት የልዩነት አጥር ራስን ሳያካልሉ በሰው ልጅነት ብቻ አንዱ የአንዱን ችግር ለማስወገድ መጣር ነበር፡፡ በሆነ አጋጣሚ አንድኛችን ከሌላኛችን በተለዬ ሁኔታ ወደአውሬነት በምንለወጥበትና እንደሳዑዲዎች አንድ ምሥኪን ወገን ላይ ቀን የሰጠንን ኃይልና ጉልበት በምናሳይበት ጊዜ በዝምታና በአግራሞት ማለፍ ሣይሆን ሃይ ብንልና ብናስቆም ተጠቃሚዎቹ ሁላችንም የሰው ዘሮች በሆንን ነበር፡፡ ሰዎች ግን ለዚያ አልታደልንምና የዘራነውን እንዳጨድን ዝንታለማችንን በየተራ ስናለቅስ እንኖራለን፡፡ ወደኋላው ላይና ቋቱ ሲሞላ ግን ሁላችንም በኅብረት የምናለቅስበት ዘመን መምጣቱ አይቀርም – ያኔ ታዲያ አልቃሽም አስለቃሽም፣ ፊሽካ ነፊም አስተኳሽም … ሁሉም ተያይዞ የደም ዕንባ እንደጎርፍ ያወርዳል፡፡ የምናስቀምጠው ነገር ሁሉ የኛው ነው – ማንም አይወስድብንም፡፡ በባንክ የምናኖረውን ገንዘብ ሲያስፈልገን አውጥተን እንደምንጠቀምበት ሁሉ በሰዎች ላይ የምንሠራውን የግፍ መዝገብም ሁሉ የምናወራርድበት ጊዜ ሲመጣ በእጃችን የገቡ ሌሎች ምሥኪኖችን ባስለቀስነው መጠንና ከዚያም በላይ እኛም እናለቅሳለን፡፡ አሁን ግን በብረት አጥር ውስጥ የምንኖርና መቼም ቢሆን ምንም ችግር እንደማይደርስብን የምንቆጥር ወገኖች አንዳችን በአንዳችን ችግር እየተዝናናን መኖርን መርጠናል፡፡ የምንመርጠው መንገድ ሁሉ ግን አዋጭ ሊሆን እንደማይችል ከታላቁ መምህር ከታሪክ መማር በተገባን ነበር፡፡ ያለቀሱ ይደሰታሉ፤ ያስለቀሱም ያለቅሳሉ፡፡

ዐረቦች በእኔ ዕድሜ ኢትዮጵያ ውስጥ በርሜል ገፊ ነበሩ፡፡ የሚገፉት በርሜልም የነዳጅ ሣይሆን የውሃ ነው፡፡ ከአምስትና ከአሥር ኪሎ ሜትሮች ከሚገኙ የወንዝና የጉድጓድ ውሃዎች በሽክናና በቅል እየቀዱ ሃዲድ በተገጠመላቸው በርሜሎች በመግፋት ለሀብታም ኢትዮጵያውያን እየሸጡ በሚያገኙት የላብ ፍሬ ይተዳደሩ ነበር – የዛሬውን አያድርገውና፡፡ ዛሬና አሁን ግን ያን መገፋታቸውን ፈጣሪ ተመልክቶ ይሄውና በየሥፍራው እንደምንጭ እየቆፈሩ በሚያወጡት ነዳጅ ጠግበው ይሠሩትን አጥተዋል፡፡ ለዚህም ያበቃቻቸው ባለብዙ ካርድ ሀገር የሆነችው አሜሪካ ናት፡፡ ገንዘብ በፍጥነት የሚገባለት ጭንቅላት ውስጥ ደግሞ የሚያስብ አንጎል አይኖርም፤ ገንዘቡ ወደ ኪስ ሲንዶለዶል አንጎል ከጭንቅላት እየወጣ ወደከርስ ወርዶ ይደበቃል፡፡ ዐረብ ደግሞ ስናየው አብዛኛው ሃይማኖት የለሽ ጥጋበኛ ነው፡፡ እንደዐረብ አስመሳይና መረን የለም፡፡ ዕውቀቱ ሣይኖር ፔትሮዶላሩ ተትረፈረፈላቸውና የሚሆኑትን አጡ፡፡ ዕድሜ ለአሜሪካ ሥልጣኔን በገንዘባቸው ከአሜሪካና አውሮፓ አመጡላቸው – ዐረቦች የዛሬ ስንት ዓመት ከተማቸውን በፍየልና በዓሣሞች ያስጸዱ እንዳልነበር ዛሬ የሀበሻ ጉልበትና የአሜሪካን ቴክኖሎጂ አጠገባቸው፡፡ እነዚህ ለይስሙላ “አላሁኣክበር” እያሉ ሃይማኖት ያላቸው የሚመስሉ ስድ ሰዎች በተለይ ሀብታሞቹና የቤተ መንግሥት ልዑላኑ የሚሠሩትንና በኪታቦቻቸው የሠፈሩትን ቀኖና ሃይማኖት ብናስተያይ ከሞላ ጎደል ሁላቸውም የሰይጣን አምላኪዎች መሆናቸውን መረዳት አይከብደንም፡፡ እነዚህ የለዬለትን ጥቁር ሰይጣን አምላኪ ዐረቦች በግልጽ ባይሆንም ብዙዎቹ በኅቡዕ ሉሲፈርን ከሚያመልኩ የሩቅ አጋዦቻቸውና የሀብት ተጋሪዎቻቸው ነጫጭባዎች ጋር እየተመሣጠሩ ዓለምን ከሃይማኖት፣ ከሞራልና ከባህላዊ ትውፊቶች አንጻር እያላሸቋት ይገኛሉ፡፡ የሁለቱም እምነት አንድ ነው፤ በገራምነት ሉሲፈር የተሻለ ቢሆንም ሲመጣበት ከሰይጣን ባልተናነሰ ቁጡ ነው፤ ለአንድ ክፋት ተመጣጣኝ ደግነት እንዳለው የሚያምኑት ሉሲፈራውያን ለጥቅማቸው ሲሉ ከሰይጣናውን በማይተናነስ ሁኔታ ዓለምን እስከመሸጥና መለወጥ ይደርሳሉ፡፡ የሁለቱም የእምነት መሠረት ገንዘብ ነው፡፡ ገንዘብ ሁሉን ያደርጋልና ሥልጣንንና ገንዘብን የተቆጣጠረ ወገን ሁሉ ያሻውን መሆንና ማድረግም ይችላል፡፡ ዴሞክራሲ፣ ፍትህና ነጻነት ጭምብሎች ናቸው – ለሁሉም እኩል የማይሠሩ የሚጠሉትን የማንበርከኪያ ካርዶችም ጭምር፡፡ ገንዘብ ካለ በሰማይ መንገድ አለ የተባለው ለጊዜውና በአሁኑ የዓለማችን ቅርጽ እውነት ነው፡፡

ገንዘብ ካለህ ዴሞክራሲን ከአሜሪካም ሆነ ከእንግሊዝ ትገዛለህ፤ ገዝተህም ለሕዝብህ ታድላለህ፤ አድለህም “ዴሞክራሲን ለሕዝቤ አደልኩ!” ብለህ ብትናገር ትታመናለህ፡፡ ባትታመንም በዴሞክራሲያዊነትህ ተቀባይነትን አታጣም፡፡ ዕድሜ ለገንዘብህ፡፡ ድሃ ከሆንክ ግን በኢዴሞክራሲያዊነት፣ በአሸባሪነት፣ በሰብኣዊ መብት ጣሸነት፣ በምርጫ አጭበርባሪነት፣ … ትወቀሳለህ፤ ወደ ጓንታናሞ ልትላክና ልትበሰብስ ዕድል ከቀናህም ወደዘሄግ የነሱው መሣሪያ ልትቀርብ ትችላለህ፡፡ በአይኤም ኤፍና በዓለም ባንክ ልምጮችም ልትሸነቆጥ ትችላለህ፤ በልዩ ልዩ ማዕቀቦችና ጠና ሲልም በኔቶ ጦርና በተናጠል የኃያላን ብትርም ልትኮረኮም ትችላለህ፡፡ ዓለማችን እንዲህ ዐይናቸውን በጨው ባጠቡና ባፈጠጡ መድሎዎች የተሞላች ናት፡፡ አንበሣ ምን ይበላል ተበድሮ ምን ይከፍላል ማን ጠይቆ  ነው ነገሩ – ግን አይምሰልህ – የቀንም ቀን አለው ፤ የጀግናም ጀግና አለው፤ ፍርድ ቢዘገይ አይቀርም፡፡ እናም ወዮ እንላለን – ወዮ ለቀኑ፡፡ ከሳዑዲና ከመሰል ጭራቅና ሰይጣን መንግሥታት አንሶላ ለምትጋፈፈዋ የሉሲፈር ሀገር ወዮላት! የ”ወዮላት!” መንስኤውም ፍርደ ገምድልነቷና ያንን ተከትሎ ቢሊዮኖች መከራና ስቃይ ውስጥ መግባታቸው ነው – ሚዛናዊ ፍርድን የማያውቅ እንዲያውቅ የሚገደድበት አጋጣሚ ይመጣለታል – ወደደም ጠላም፡፡ ይህች ሀገር የምትለውንና የምትሠራውን አጥኑ፡፡ ያለባትንም ወዮታ ልብ በሉ፡፡ የአሁኑንም ብቻ አትመልከቱ፡፡ ለዚህ ለዚህማ ኢትዮጵያም በዓለም ከነበሩ አራት ኃያላን መንግሥታት አንዷና እስከየመንና ከዚያም ባለፈ  የምታስገብር ታላቅ ሀገር ነበረች፡፡ ብዙ የአሁን ነገሮች ታሪክ የሚሆኑበት፣ ብዙ የወደፊት ነገሮችም የአሁን የሚሆኑበት ዕፁብ ድንቅ ሁኔታዎች ይከሰታሉና እንዳለ የሚቀር፣ እንደቀረም የሚኖር ነገር አለመኖሩን ማስታወስ ይገባል፡፡ ይህች ቀን በቅርብ ታልፋለች፡፡…

በልጅነቴ ቤተሰብ ወደሱቅ ሄጄ ዕቃ እንደገዛ ይልኩኝ የነበረው “ዐረብ ቤት ሄደህ ይህን ዕቃ ገዝተህ ና!” እንጂ ወደሱቅ ሂደህ ይህን ወይ ያን ግዛ አይሉኝም ነበር፡፡ በ”ሰይቼንቶ ሄድኩ” ይባል የነበረውና አሁንም ድረስ በአንጋፋ ዜጎች የሚባለው የመጀመሪያዋን የጣሊያን ታክሲ መኪና እንደሚያስታውሰን ሁሉ ዐረብ ቤትም የሚያስታውሰን የሱቅ ሸቀጦች ይበልጡን በዐረቦች መጀመራቸውን ወይም በነሱ ይካሄዱ የነበረ መሆኑን ነው፡፡ ኢትዮጵያ ከእኛም በላይ የነሱ ቤት ነበረች፡፡ “ፈረስት ሂጅራ”ን ትተነው ትናንትናና ከትናንት ወዲያ በነገሥታቱ ዘመን የአሁኗ ኢትዮጵያ በልጽገውና ከብረው ከእኛው ባልተናነሰ እንዲያውም በበለጠ እየተዘባነኑ የሚኖሩባት የእኩል ሀገር ነበረች – ለነገሩ ኢትዮጵያ ለውጪዎች እንጂ ለራሷ ልጆች ሆና አታውቅም – ሀገራችን ብዙውን ጊዜ የሚጠቅማትን ከማይጠቅማት ያለመለየት ችግር አለባት፡፡ ዛሬ ወያኔ የሚባል ሀገር አጥፊ አንበጣና ተምች መላዋ ሀገራችንን ቀስፎ ስለያዛት የተለዬ ውርደት ገጠመንና ለዚህ ውርደት ተዳረግን እንጂ ዐረቦች ልብ ኖሯቸው እንዲህ ሊጫወቱብን የሚቃጡ አልነበሩም፡፡ ጊዜ ነው፡፡ ጊዜ ሁሉም ነገር ነው፡፡ ‹ጊዜ ባለውሉ› ሁሉንም ያሳያል፡፡ … ዕድሜ ከሰጠን ደግሞ ወደፊት ይህን ሂሳባቸውን ሲያወራርዱ እናይ ይሆናል፡፡ አንድዬን ለበቀልና ለአጸፋዊ ምላሽ ማን ብሎት? አሁን አሁንስ ፈጣሪ ለዚህ ተግባር ብቻ ያለ ይመስለኛል – ለቅጣትና የኃጢኣት ዋጋን ለመስጠት፡፡

የሆኖ ሆኖ ግን ኢትዮጵያዊ መንግሥት ስለሌለን እየደረሰብን ያለው ይህ ግፍና ቅጣት በኛ ላይ ብቻ የወረድ የውርደትና ቅሌት መዓት ሣይሆን በሰው ልጆች ላይ እየደረሰ ያለ መቅሰፍት መሆኑን ልብ ማለት ይገባል፡፡ በሳዑዲ አንድ ዜጋ አለኃጢኣትና አለወንጀል ኢትዮጵያዊ በመሆኑ ብቻ በጠራራ ፀሐይ ታረደ ማለት የታረደው ሰው በሃይማኖትና በፆታ ወይም በመልክዓ ምድር ሳይወሰን ነጭም ነው፤ ጥቁርም ነው፤ ቢጫም ነው፡፡ አለፍርድና አለአበሳው የታረደው ሰው ሁሉንም የሰው ዘር የሚወክል እንጂ አንድን ሀገር ብቻ ለይቶ፣ የአንዲትን ሀር ዜጎች ብቻ አጣቅሶ በውርደት የሚያስጠራ ክልላዊ ወይም ብሔራዊ ጉዳይ ብቻ አይደለም፡፡ ይህን ማድረግ ድፍረት እንጂ ሌላ ባለማስፈለጉ በማንም ላይ እንዲህ ማድረግ ቀላል ነው፡፡ በአሳቻ ቦታ አንድን ነጭ አሜሪካዊ ማረድ ወይም ጠቃሚ የሰውነት ብልቶቹን እያወጡ ለሀብታም መሸጥ ቀላል ነው፡፡ በአሳቻ ቦታ አንድን ነጭ እንግሊዛዊ ወይ ሞስኮባዊ ማረድ ቀላል ነው፡፡ በተመቸ ሥፍራ አንድን ነጭ እስራኤላዊ አንቆ በከንቱዎች ዘንድ መዘባበቻ ማድረግ ቀላል ነው – በአልቃኢዳዎች ሲደረግ የነበረም ነው፡፡ አደጉ ከተባሉ ሀገራት የተመለመሉና አንቱ በተባለ ዘመናዊ የጦር ሥልት ሠልጥነው ለግዳጅ የተሠማሩ “የሰለጠነው ሀገር” ወታደሮች ኢራቅ ውስጥ ሬሣ ላይ ሲሸኑ አይተናል፤ ያኔም በዓለም የሥልጣኔ ደረጃ “ምጥቀት” ተደንቀናል – ከዚህች ሰዎች ሰዎችን ከምድረ ገጽ ሊያጠፉ አሰፍስፈው ከሚታዩባት፣ የሞተ ሰውን ሳይቀር በ”ማሰቃየት” ሰይጣናዊ እርካታ ለማግኘት ከሚማስኑባት ከዚህች ድውይ ዓለም፣ ሳዑዲዎች እየፈጸሙት ከሚገኘውና ከመሳሰለው አረመኔነት ሌላ ምን ይጠበቃል? ዕውር ዕውርን እየመራው ገደል እንጂ ገነት አይጠበቅም፡፡

በመሠረቱና በእውነትም ብዙ ክፉ ነገሮችን ማድረግ በጣም ቀላል ነው፡፡ ዋናው ነገር ልክ እንደጥጋበኞቹ ዐረቦችና ተባባሪዎቻቸው ወያኔዎች ኅሊናን የመሳትና ወደአውሬነት የመለወጥ ጉዳይ ነው፡፡ በዚህ ሂደት ተዋራጁ ጨካኙ አውሬና ሰብኣዊነት በአጠቃላይ እንጂ የሚታረደውማ ዋናውን የዕልቂት በርኖስ ተከናንቦት እያለ የምን ውርደትን መደረብ ነው? እውነትን መነጋገር ከተፈለገ እንግዲያውስ የታረደ ከበረ፡፡ የታረደ በፈጣሪ ዘንድ የሰማዕትነትን ካባ ተጎናጸፈ፡፡ በከንቱ ጭዳ የሆነ የዘላለም ክብርን አገኘ፡፡ ተጠየቁ እንደዚህ ነው፡፡ የተዋረደው እዳር ቆሞ “አይዞህ ወንድሜ እረዳቸው፤ ቀብጠዋልና ጉልበትህን አሳያቸው፤ እኛን ጠልተው ከሀገር ስለወጡ ቀኝ እጃችንን አውሰንሃልና እንደፈለግህ አድርጋቸው” እያለ በስቃይ የሚደስት ወገን ነው፡፡ ጊዜው ሲደርስ ወዮ ለዚህ ዓይነቱ ፍጡር! እናም ውድ ኢትዮጵያውያን ለቅስቀሳ ፍጆታው ያህል ልክ ነው ኢትዮጵያና ኢትዮጵያውያን ተዋርደናል፤ ተንቀናል፤ ከዚያም በላይ፡፡ እንደእውነቱ ከሆነ ግን የተዋረደው ዓለም ነው፤ የተናቀው የሰው ልጅ ዘር በአጠቃላይ ነው፤ የታረደው በትዕቢትና በዕብሪት አንገታችንን እየቆለመመ በሠይፍና በጎራዴ እየቀነጠሰን ያለው በሌላኛ ጠርዝ የሚገኘው የሰይጣን አሽከርና ሎሌ የሆነው የሰው ልጅ ነው፡፡ እንጂ ኢትዮጵያማ በአሁኑ ሰዓት በጽርሓ አርያም ከሁሉም በበለጠ ክብርና ሞገስ እየተሸሞነሞነች ናት፡፡ የዚህን አያዎኣዊ(paradoxical) አነጋገር አንድምታዊ ፍቺ ወደፊት ምናልባትም በቅርብ የምናየው ይሆናል፡፡ … የተዋረድን የመሰልነው ደግሞ በውጭ ብቻ እንዳልሆነ እናውቃለን፡፡ ወያኔ እስካለ ክብር የለንም፤ ከነአካቴውም እንደሰው አንቆጠርም፡፡ የሁሉም መጫወቻ ነን፡፡

እንደብዙዎች ዜጎች ኢቲቪን አልመለከትም፡፡ ስመለከት በሽታየን የሚቀሰቅስ አንዳች ነገር ስለማገኝ አላይም – ስህተት ነው – ግን ምን ላድርግ፤ ከጤና የሚበልጥ ነገር ደግሞ የለም፡፡ ዛሬ ለምሳሌ ትልቅ በሽታ ነው የተቀሰቀሰብኝ፡፡ ወደሌላ ጣቢያ ላልፍ ስል ድንገት ኢቲቪን ስከፍት ኃይለማርያም ደሳለኝ የሚባለው ዳግማዊው መቶ አለቃ ግርማ ወ/ጊዮርስ በወቅቱ የወገኖቻችን አሰቃቂ ጉዳይ በ”ጋዜጠኛ” እየተጠየቀ አየሁ፤ ኃይለማርያም ደንቆሮና በልጆች ቋንቋ ጀዝባ መሆኑን ዛሬ ከእስከዛሬው  በበለጠ ልብ አልኩ፡፡ ራሴን እንደምንም አሳምኜ ትንሽ ልከታተል ወሰንኩና ማየቴን ቀጠልኩ፡፡ ግን የጋዜጠኛ ተብዬውና የሰውዬው የአቀማመጥ ሁኔታ ራሱ ትልቅ የፕሮቶኮል ችግር ስላለበት መከታተል አትበሉት – እየቀፈፈኝ እንደምንም ለጥቂት ደቂቃዎች ታገስኩና ተከታተልኩ፡፡

ጋዜጠኛው ጠቅላይ ሚኒስትር፣ ጠቅላይ ሚኒስትር ተብዬው ደግሞ ጋዜጠኛ መስለዋል፡፡ ጋዜጠኛው እግሮቹን አጣምሮ ተንቀባርሮና እጅግ ተዝናንቶ ‹ሲጠይቅ›፣ ኃ/ማርያም እግሮቹን በሥርዓቱ ዘርግቶ ሽቁጥቁጥ እያለ ሲመልስ አንጀትን ይበላል – በ”ሥርዓቱ” ባልኩበት መንገድ መቀመጡ ጥሩ ሆኖ የ“ጋዜጠኛው” “ጠቅላይ ሚኒስትራችን”ን በማንጓጠጥ መልክ እግሮቹን አጣምሮ መጠየቁ ነው የቆጨኝ – በጠቅላይ አሽከሩ አማካይነት የናቁን ግብጾችና ሳዑዲዎች ብቻ ሣይሆኑ ጋዜጠኞቻችንም ናቸው ማለት ችያለሁ፤ ወያ በሚያገኘው አጋጣሚ ሁሉ ኢትዮጵያን ለማዋረድ የማይፈነቅለው ድንጋይ አለመኖሩን ስረዳ የወያኔን ሥነ ልቦናዊ ደዌ የክብደት ደረጃና የኛን የምሕረት ዘመን መንቀራፈፍ አስታውሳለሁ፡፡ ይህ ነገር መለስን እንዳንረሳ ሲባል በወያኔዎች ሆን ተብሎ የተቀናበረም ይመስላል፡፡ የሚናገረውን ብቻም ሣይሆን እንዴት መቀመጥ እንዳለበትም መመሪያ ቢጤ ሳይሰጡት አልቀረም፡፡ ቤተሰቤ በሙሉ ነው በዚህ ነገር የተሸማቀቀው፡፡ በርግጥም አቶ መለስን አስታወስነው – ተሳክቶላቸዋል፡፡ አቶ መለስ ‹ጋዜጠኞቹን› እንዴት እንደሚገላምጣቸውና አጥንተው ከመጡት ይጠይቁትን ያሳጣቸው እንደነበር ትዝ አለኝ፡፡ ከመሞቱ አጎደለን ማት ነው? በርግጥም እኮ መለስ ቢኖር ኖሮ ሳዑዲዎችም ይህን ያህል አይማግጡም ነበር ብሎ መገመት ይቻላል፡፡ በርግጥም እኮ መለስ ቢኖር ኖሮ ግብፆች በኃ/ማርያም ላይ እንዳፌዙበት በርሱ ላይ አያፌዙበትም ነበር፡፡ ስለዚህ ወያኔ የቀረው ጊዜ አንድ ወርም ይሁን አንድ ዓመት ለምን ጠቅላይ ሚኒስትሩ አንዱ ወያኔ አይሆንልንም? እውነቴን ነው – እንደለመድነው አንዱ ትግሬ ቁጭ ይበልበትና ይህን ኮንዶም ሰውዬ ወደማስተማር ሙያው ይመልሱት፡፡  “ውርደታችን” እኮ ለከት አጣ፡፡ በንነው እስኪጠፉ ድረስ  በዚህች እንኳን አንዋረድ፡፡ በአሁኑ ሰዓት እኮ ኢትዮጵያውያንን እንደውዳቂ ዕቃ የማይቆጥርና እንደጠፍ አህያ ልቡ እስኪጠፋ የማይጭን የለም፡፡ እስኪያልፍ ያለፋልና አይዞን!!!

በቅድሚያ ይህ ሰውዬ ብዙዎች እንደሚሉትና በብዙዎች እንደሚታመነው ከአንድ ሀብታም ሰው የቤት ጠባቂ ያነሰ የስብዕና ደረጃና የሥራ አፈጻጸም ሥልጣን ያለው መሆኑ ፀሐይ የሞቀው ነገር ነው፡፡ የዚህ ሰውዬ ጭንቅላት ሥሪት ምን እንደሆነ ግራ የሚያጋባ በመሆኑ እንጂ እኔ እሱን ብሆን እንደዚህ መሣቂያና መሣለቂያ ሆኜ መኖርን አልመርጥም ነበር – የሰው ተፈጥሮ ግን በውነቱ አስገራሚ ነው፡፡ ከኃይለማርያም ደሳለኝ ይልቁንስ የፍቅር እስከመቃብሩ ፈረጃ ይሻላል፤ “ፈረጃ በሚለው የባሪያ ስሜ የሚያውቀኝ ሰው ምን ይለኛል?” በሚል መዘባበቻ ያደርገኛል ብሎ የፈራውን ዕዝራ የሚለውን አዲሱን ስሙን ለመቀበል ፈቃደኛ አልሆነም – ባህሉንና ማኅበረሰብኣዊ አወቃቀሩን ተረድቶታልና የሰው የሃሜት ግርፋት አስቀድሞ የታዬው ይመስላል፡፡ (ይህን ስል ነገሮችን ለንጽጽር አስቀመጥኩ እንጂ ፍርድ ውስጥ እንዳልገባሁ ማስታወስ እፈልጋለሁ)፡፡ በዚህ መልክ እየተሸቆጠቆጠ አንድም የራሱ ቃል ሳይኖረው (with out any say in ‘his’ government) የሰጡትን የሚያስተላልፍ አሸንዳ ሆኖ መኖሩ ምን ዓይነት እርካታና ደስታ እንደሚያገኝበት አይገባኝም፡፡ አለኝ ከሚለው ሃይማኖትም ሆነ ከራሱ ኅሊና ጋር እንደተጣላ እስከመቼ በሌሎች ሰዎች ጭንቅላት እየተመራ – ለቃሉ አጠራር ይቅርታ ይደረግልኝና – ኮንዶም ሆኖ እንደሚኖር አላውቅም፡፡ ራሱ ነጻ ቢወጣ ይሻለዋል፡፡ ኃይለማርያም ራሱን ቢሆንና በነጻይቱ ኢትዮጵያ ባሰኘው የሥልጣን እርከን ተወዳድሮ በራሱ አእምሮ የሚንቀሳቀስበትን መድረክ ቢጠብቅ፣ ለዚሁ መድረክ እውንነትም የበኩሉን ትግል ቢያደርግ እንደሚሻለው በዚህ አጋጣሚ ብጠቁም ብዙ የዘገየሁ አይመስለኝም፡፡ ካሰበበት ይችላል፡፡ አሁን ካለበት የጥፋት መንገድ ግን በአፋጣኝ ይውጣ፡፡ ክፉኛ መሽቷል፡፡ ወያኔ ድቅድቅ ጨለማ ውስጥ የሚዳክር፣ በራሱ ኃይልና ጥበብ ሳይሆን በአጋጣሚዎች መወሳሰብ ብቻ እስትንፋሱ ብን ብን እያለች የሚኖር ድርጅት ነው፡፡ እንደሚመስለኝ ወያኔ እንዳይወድቅ እያገዘው ያለው የጥቂቶች ብፁዓን አባቶች ጸሎት ነው፤  መውደቁን የምንመኘው ዜጎች ራሳችንን ሳናስተካክል እንዲሁ በባዶ ሜዳ ርስ በርስ እየተናቆርን በምንገንበት ሁኔታ ወያኔ አሁን ቢወድቅ ጦሱ ብዙ፣ መዘዙም በቀላሉ የማይወገድ ነው፡፡ በመቶዎች የተከፋፈለ ፖለቲከኛ፣ ለሥልጣን የቋመጠ ጎጠኛ፣ በዘር የተቧደነ ጦረኛ፣ ለበቀል ያሰፈሰፈ ሸፍጠኛ፣ ለሀብት የተስገበገበ ሆዳም፣ … በየጉራንጉሩ አንዳች ዕድል በሚጠባበቅበት ሁኔታ ይህ በቁሙ ሞቱን ጨርሶ ጣር ላይ ያለ የማፊያ ቡድን ለይቶለት እንዳይወድቅ እኔም ብጸልይ የሚኮንነኝ እንዳይኖር እማጠናለሁ፡፡ መውደቅ ያለበትን ጊዜ በበኩሌ አውቃለሁ፡፡ ያም ቀን አሁንና ዛሬም ሊሆን በቻለ፡፡ ግን ፈጣሪ የታከለበትና ሌላ አደጋ የማያስከትል እንዲሆን የምንመኝ ብቻ ሣይሆን በርትተን የምንጸልይ ወገኖች አንጠፋምና ጌታ ይሰማናል፡፡ ችግሩ የመንግሥት ለውጥ አይደለም፡፡ መንግሥት መቼም ሊለወጥ ይችላል፡፡ ዋናው ነገር ‹አሮጌው ወይን በአዲሱ አቅማዳ እንዳይገባ› የመጠንቀቅ ጉዳይ ነው – ለኢትዮጵያ ደግሞ ከሰው በላይ የሚጠነቀቅላትና የሚጨነቅላት አምላክ አላት፤ እንደሰው ቢሆንማ እስካሁን ድረስም ቢያንስ በሕይወት መቆት ባልተቻለን ነበር – ወርቁ ጠፍቶ ሚዛኑ ያለው በአንድዬ ተራዳኢነት ብቻ ነው – ይህን አንተ ላታምን ብትችል አልፈርድብህም – ምክንያቱም የሰቆቃው ዘመን በእጅጉ በመራዘሙ ሳቢያ ከአምላካችን ጋር የተጣላን ዜጎች ቁጥር ብዙ መሆኑን መገንዘብ አያስቸግርምና፡፡ እንጂ በመሪና በመንግሥት መለወጥማ መንግሥቱስ በመለስ ተተክቶ አልነበረምን? እናም በዚህ አምናለሁ – ወያኔን መጣል የሴከንዶች ጉዳይ ነው፡፡ እንዲያውም ሴከንዶችንም ላይፈጅ ይችላል፡፡ ዱሮውን የወደቀ ነውና – የታመመ ሰው ሲሞት እኮ ሳይተጣጠብ፣ ሳይከፈንና ሳይበጃጅ መሞቱ ለቤተሰብ ተነግሮ እንዲለቀስ አይደረግም፤ የወያኔም ነገር እንደዚሁ ነው – ከሞተ ቢቆይም ገናዥ እስኪገኝ – ገናዦች እስኪስማሙና ወደሬሣ ክፍል ደፍረው እስኪገቡ ድረስ ኅልፈቱ አይነገርም፤ “እባብ ልቡን ዐይቶ እግሩን ነሣው” – ወያኔም እንደ እባብ አናቱን ተቀጥቅጦ እንደድመት በዘጠኝ ነፍስ፣ ከዘጠኙም በመጨረሻዋ ይኖራል – “የተበዮች አለመስማማት ለበዮች ይመቻል”፡፡ አሁን የሚታየው ትልቁ ነገር ወያኔን ሥልጣን የሚረከበው አጥቶ ራሱንም በሚገርመው አኳኋን ሀገሪቱ ሰው አልባ ሆና መቅረቷ ነው – ይህ ካልሆነ በስተቀር ወያኔ አልሞተም ተብሎ ሊዋሽ የሚችልበት አንድም ሀገራዊ ሁኔታ የለም፡፡ ይህም ሥራ የተሠራው በደርግ፣ በወያኔ በራሱና የኢትዮጵያን ኅልውና በማይፈልጉ የውጭ ኃይሎች ነው – ኢትዮጵያ ከአናት ተመታች – ለጊዜው እስትንፋሷ ፀጥ አለና የሞተች መሰለች፤ “hibernate” ባደረገው ሕይወት ያለው በድኗም ላይ ወያኔ እንደልቡ ተንጎማለለባት – የማይቀር ፍርድ ነበረና እንደምንም ተወጣነውና ይህም ክፉ ቀን ሊያልፍ የምሥራቹ ደረሰ፡፡ ፈጣሪ እሾህ አሜከላውን ሲገፍላት፣ ይህን የ80 ሚሊዮኖች የአስተዳደር ወንበር ሊረከቡ የሚችሉ የበቁ ዜጎች ፈጣሪ ፈልጎ ሲያገኝና ከያሉበት ሲያሰባስብ ኢትዮጵያ ምን በመሰለ ክብርና ሞገስ እንደምትነሣ ለማየት ያብቃን፡፡ እንዲህ በል አለኝ እንዲህ አልኩ፡፡ በትንሣኤዋ የሚፈራ ይፍራና ይውጣለት፡፡ የማይቀርን መናገር ነውር አይደለም፡፡ ሞቶ መነሳት በግለሰብ እንጂ በሀገር ደረጃ በጣም ቀላል ነው፡፡ ሞቶ ያልተነሳ ሀገር የለም፡፡

ኃ/ማርያም ከተናገረው ፍሬፈርስኪ አንዱ አስገርሞኛል፡፡ በዚህ በወቅቱ የዜጎቻችን በ‹ቅጡ አለመያዝ› ምክንያት ስለሳዑዲና ኢትዮጵያ ወዳጅነት መጠልሸት መቻል አለመቻል ሲጠየቅ “በዚች ክስተት፣ በዚህች ትንሽ ነገር” በማለት ይህን በሙሉጌታ ሉሌ አነጋገር – ቃል በቃልም ባይሆን ጭብጡን ልጥቀሰው – “ይህ ሳዑዲ ዐረቢያ ውስጥ በሀገራችን ዜጎች ላይ የተከሰተው ዕልቂትና ስቃይ መንግሥት ቢኖረን ኖሮ ጦርነት የሚያሳውጅ ታላቅ ሀገራዊ ጉዳይ ነው፤ ብዙ የዓለም ጦርነቶች የተቀሰቀሱት ከዚህ በሚያንሱ ትናንሽ አጋጣሚዎች ነው፡፡ ይህ የኛው ጉዳይማ ወዲያውኑ ክተት የሚያስብል ነው፡፡…” ተብሎ የተመሰከረለትን ሀገራዊ ታላቅ ጉዳይ እንደተራ የጎረቤት ጠብ ቆጥሮት ዐረፈው፡፡ ያኔ የዚህን ሰውዬ ኢትዮጵያዊነት ብቻ ሳይሆን አእምሮኣዊ ጤንነቱንም ተጠራጠርኩ፡፡ አቶ መለስ  እንደዚህ ያሉ ጀዝባ ሆዳሞችን፣ እንደደመቀ ያሉ ደናቁርት ጌኛዎችን መርጦ አጠገቡ ማስቀመጡ ለወያኔው ሥርዓት ዕድሜ መራዘም በርግጥም ጠቅሞታል፡፡ እናላችሁ ይህን ላንቃችን እስኪበጠስ እያስጮኸን የሚገኘውን ታላቅ ጉዳይ፣ ደም እስክናነባ እያስለቀሰን የሚገኘውን የሚሌንየም ሰቆቃ እንደቀላል ነገር ቆጥሮ “በዚች ክስተት ወዳጅነታችን አይሻክርም…” ብሎን ዕርፍ፡፡ ይህ – በነሱው ቃል – ወደር የማይገኝለት ተንበርካኪነት ወያኔዎች ከሕዝብ ስለተጣሉ ከዐረቦቹም ጋር ላለመቀያየምና  በል ልዩ ሰበብ አስባቦች ከነዳጁ ዶላር ለመመጽወት ካላቸው ጽኑ ፍላጎት የሚመነጭ እንጂ ኢትዮጵያዊ መንግሥት ቢኖረን ኖሮ ሰው አይደለም አንዲት ጥንቸልም ብትገደልብን ብሔራዊ ጦርነት ያሳውጃል፡፡ አንደኛውን ይሁን ሁለተኛውን የዓለም ጦርነት የቀሰቀሰችው እኮ አንዲት ዓሣማ ናት አሉ፡፡ እንዲያው ለነገሩ ግን በወገን ደም ለመቀለድ ይህን ያህል ድንቁርናና የገረረ ቆዳ ከየት አመጡት? በዘርና በቋንቋ ተመሥርተው በስቃይ ላይ ከሚገኙ ወገኖች የራሴ ናቸው የሚሏቸውን ዜጎች እየመረጡ ወደ ሀገር መመለስንስ እንዴትና ከየትስ ተማሩት? የበረሃው ወያኔ ከ23 ዓመታት በኋላ እንዴት ይህን ዓይነቱን የጫካ የመድሎ አሠራር አይረሳም? ቂም በቀልንና የነገር ቁርሾን ለአፍታም እንዳይዘነጉ ምን ዓይነት ሶፍትዌር ይሆን በየጭንቅላታቸው ያስገጠሙት? ለነሱም ሆነ ለኛ  ምን ዓይነት መረገም ይሆን? የሚመለሱትን ብዙዎቹን ስትመለከቱ እኮ የሕወሓት የጦር ባታሊዮን ይመስል ቋንቋቸው … ምንም ይሁን … ያው ግን ወገኖቻችን ናቸውና ምን ይደረጋል፤ ሀዘናችንና ልቅሶኣችን ቅጥ አጣ – ሟቹም ገዳዩም እቤቷ መሽገውባት አትስቀው አታለቅሰው  ነገር ሆነባትና ግራ ገብቷት እንደተቸገረችው ያቺ ምሥኪን ወይዘሮ ሆነናል፡፡ ብቻ ግን ከዚህ ሁሉ የመንግሥትነት ዘመን በኋላ እንደዚህ ያለ አድልዖ ሲታይ ክፉኛ ያምማል፡፡ በዚህ የግሎባላይዜሽን ዘመን የሰው ዘር ስለሰው ዘር መጨነቅ ሲገባው ሊያውም የሁላችን የምንለው  መንግሥት የኤምባሲዎቻችንን ሥራና ባጀት ለራሱ ሰዎች ብቻ ማዋሉ ከማሳዘን ያለፈ የሀገር ሸክምና ዕዳ ነው፡፡   ሌላው ኢትዮጵያዊ በዐረቦች እንዲጨፈጨፍ ተትቶ የራስ የሚሉትንና መዋጮና ድጋፍ ያደርግ የነበረን እየመረጡ ከእሥር ማስፈታት፣ ቅድሚያም ሰጥቶ ወደሀገር ማስገባት … ነገ የሚያመጣውን የዞረ ድምር ካለማየት የሚመጣ ድንቁርና ነው፡፡ አቤት የዚህ ዘመን ትንግርት! እግዚአብሔር ሆይ ቶሎ ናልን!!

 

yiheyisaemro@gmail.com

Pen

 

↧

የስብሰባ ጥሪ በኔዘርላንድ ነዋሪ ለሆኑ ኢትዮጵያውያን በሙሉ

$
0
0
↧

የኛ ነገር፡ ክፍል 20፤ ሰይፋችንን አጥተነው፤ ሰልፋችንንም ልንቀማ ?? (ከተክለሚካኤል አበበ )

$
0
0

ከ ተክለሚካኤል አበበ

የሳኡዲ ግፍና የኛ ሰልፍ፤

እንደመግቢያ፤ የፋና ነገር

  1. ፋና፤ ኢትዮጵያዊ ካናዳዊት ነች፡፡ ቆንጆ ነች፡፡ እሱዋ እንደምትለው ከሆነ ፖለቲካ አትወድም፡፡ በአባይ ቦንድ ሽያጭና በመሰል የመንግስት መርሀ ግብር ዝግጅቶች ላይ ግን ቀድማ የምትገኝ ጎበዝ ነች፡፡ በውጭ አገር የሚገኙ ተቃዋሚዎች መፈክር ይዘው በኢህአዴግ ላይ ሲሰለፉ ስትመለከት ግን ደምዋ ይፈላል፡፡ ሰሞኑን በዚህ በሳኡዲአረቢያ በሚገኙ ኢትዮጵያዊያን ላይ የደረሰው ግፍ ስላሳዘናት፤ ሳውዲዎችን ልክ ልካቸውን ልትነግራቸው ቆርጣ ተነስታለች፡፡ ስለዚህም በመጪው አርብ መሰል ጉዋደኞችዋን ይዛ ሰልፍ ልትወጣ ተፍ ተፍ ትላለች፡፡ በፋና እምነት በሳኡዲ በኢትዮጵያዊያን ላይ የደረሰው ሰቆቃ፤ ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር የሚያገናኘው ምንም ነገር የለም፡፡ ስለዚህ የሰልፉ እንዱ ደንብ በምንም አይነት መልኩ የኢትዮጵያ መንግስት ስም በክፉ አይነሳም የሚለው ነው፡፡ ሰናይም ወንዱ ፋና ነው፡፡ እንደፋና ያምናል፡፡ ከፋና ለየት የሚያደርገው ነገር ቢኖር፤ ኢትዮጵያውኑን በግዜ ባለመርዳቱ የኢትዮጵያን መንግስት የሚመለከተው ቢሆንም፤ የኢትዮጵያን መንግስት የሚያወግዙ መፈክሮች ማንገብ ይከፈፍለናል ባይ ነው፡፡ በተወሰነ በሰሞኑ ሰልፎች የገረመኝ፤ ያሳሰበኝ፤ ያቃጠለኝም ነገር ይሄ ነው፡፡
  1. የሳኡዲን ግፍ ተከትሎ፤ ኢትዮጵያዊያን ሁሉ ቁጣቸውን ገልጸዋል፡፡ ብዙ ሰዎች ሰዎች ይሄንን የሳኡዲን ግፍ ተከትሎ በየከተማው የሚገኘውን ተቃውሞ በመገናኛ ብዙሀን በመመልከት በኢትዮጵያዊን አንድነትና መደጋገፍ የረኩ፤ በተቃውሞው ግዝፈትም የተደሰቱ ይመስላል፡፡ እኔ ደግሞ በየስፍራው ከሚታዩት ተቃውሞዎች ጀርባ የተደበቀውን ፍርሀት፤ ጥርጣሬና ድንቁርና ስመለከት፤ እጅግ አዝኜ ልጽፍ ነው፡፡ ስለተደፈሩና ስለተገደሉ፤ ስለተዘረፉና ስለተገረፉ ኢትዮጵያውን በበቂ ስለተዘገበ ስለነሱ አልጽፍም፡፡ በነሱ ላይ በደረሰውና በኛ በውች በምንገኝ ኢትዮጵያዊያንና ኢትዮጵዊ ድርጅቶች በኩል ስለታየው ምላሽ እንጂ፡፡ ከኒው ዮርክ እስከ ሲያትል፤ ከኦታዋ፤ እስከ ከቶሮንቶ እስከ ቺካጎ … ያለውን የተቃውሞ ሰልፎችናና የተቃውሞዎቹን አፈጣጠር እንዲሁም አካሄድ በጥልቀት የተመለከትን እንደሆን፤ ከቁጣው ጀርባ የሚያሳስብና ርምጃ ሊወሰድበት የሚገባ ነገር አለ፡፡ አንዳንዶቹ ሰልፎች የኛ አልነበሩም፡፡ የነሱ እንጂ፡፡ ኮሚቴ ለማቁዋቁዋም ላይ ታች ስንል ተመለከተም፤ ከ23 አመታት በሁዋላም ይሄንን መሰል ግፍ ለመቃወም የሚያስተባብር ቁዋሚ ተቁዋም አለመኖሩም አሳዛኝ ነው፡፡

ቶሮንቶ፡

  1. በቶሮንቶ በዚህ በሳኡዲ ግፍ ጉዳይ ላይ፤ እስካሁን አራት ሰልፎች፤ አንድ ሕዝባዊ ስብሰባ ተደርገዋል፡፡ የመጀመሪያው የተቃውሞ ሰልፍ የተጠራው የአካባቢውን የሙዚቃ ባለሙያዎች ተገን ባደረጉ፤ ሰልፍና ፖለቲካ መደባለቅ የለባቸውም በሚሉ ግለሰቦች ነበር፡፡ ተቃውሞው ሙሉ በሙሉ በሳኡዲ ላይ ነው፡፡ ሁለተኛው ሰልፍ የተጠራው ደግሞ ሕወሀትን በሚቃወመው ወገን ነበር፡፡ ሁለቱም ሰልፎች የተጠሩት ባንድ ቀን ነው፡፡ በሰልፉ እለት፤ የሁለተኛው ሰልፍ ጠሪዎች ሰልፋቸውን አስቀድመው ጨርሰው ወደአንደኛው ሰልፍ ወርደው ሰልፉን በተቃውሞ መፈክሮች ባያጥለቀልቁት ኖሮ፤ መጀመሪያ የተጠራው ሰልፍ ኢትዮጵያዊያን ከአገራቸው ስለሚፈነቅላቸው ስርአትም የሚቃወም ሳይሆን፤ የሳኡዲን ግፍ ብቻ አውግዞ የሚለያይ ይሆን ነበር፡፡ ምክንያት፤ ከላይ በአንቀጽ አንድ የጠቀስኩትና ሌሎች ተያያዥ ምክንያቶችም፡፡ ግፍ ግፍ ነው፡፡ በሳኡዲም ይፈጸም በጋንዲ፤ በመለስም ይፈጸም በዳዲ፤ ግፍ ግፍ ነው፡፡ ፖለቲካ አንወድም ወይንም ፖለቲካ እንፈራለን በሚሉ ወገኖች ዘንድ ግን ይሄ ግንዛቤ ያለ አይመስልም፡፡ ቢኖርም፤ እነዚህ ሰዎች፤ የራስ-መንግስት ግፍ ተቀባይነት አለው አይነት የሞራል አስተሳሰብ አላቸው፡፡ ፖለቲካና ሰብአዊ መብት የተለያዩ ናቸው አይነት ነገር፡፡
  1. የቶሮንቶውን በተመለከተ፤ በሰልፉ ላይ ትንታግ ሆና የዋለች እህት፤ ይሄንን ፖለቲካና ሰብአዊ መብት አትደባልቁ ስልት በተመለከተ እንዲህ ስትል ጽፋለች፡፡ Just to let you know all, this is the new trend TPLF has started now, they organize protests before activists do … Please, also spread this word and warn innocent Ethiopians not to be used in every media outlet available. Jiraf erasu gerfo, erasu yichohal, sad. አዲሱ የህወሀት ስልት፤ የምጣዱ እያለ የእንቅቡ ተንጣጣ አይነት ነገር፡፡ ወይም ጅራፍ ራሱ ገርፎ ራሱ ይጮሀል፡፡ የዋህ ኢትዮጵያዊያን እንይሸወዱና መጠቀሚያ እንዳይሆኑ ለመገናኛ ብዙሀን አሳስቡ፤ ስትል ተናግራለች፡፡

 

ኒውዮርክ፤ ሺካጎ፤ ኦታዋ

  1. አንድ የኒው ዮርክ ሰው እንደጻፈው፤ ሌላ የቺካጎ ሰውም እንደዘገበው፤ የኦታዋ ጋደኞቼ እንደነገሩኝ ከሆነ፤ በኦታዋ፤ በሺካጎና በኒው ዮርክም የሆነው ተመሳሳይ ነው፡፡ ለምሳሌ፤ አቶ አለማየሁ በሁሉ ከኒው ዮርክ እንዲህ ብሎ ጽፎዋል፡ The demonstration was organized by pro-Woyanne, but overtaken and led by anti-Woyanne group which included loud verbal disagreement and some shoving, pushing between the 2 groups for few minutes:: ሰልፉ የተዘጋጀው በአፍቃሬ መንግስቶች ነበር፤ ነገር ግን ከጥቂት አተካሮ በሁዋላ አፍቃሬ ዴሞክራሲዎቹ ቀሙት እንደማለት ነው በግርድፉ፡፡ ሺካጎዎች ለጊዜው የተረቱ ይመስላል፡፡ የረዥም ግዜ የሺካጎ አካባቢ ተሙዋጋች አቶ አበራ ሲሳይ ስለሺካጎ ተሞክራቸው እንዲህ ብለው ጽፈዋል፡፡ We in Chicago tried to do the same but overtaken by a group named “hand to hand” .We proposed that we collectively denounce the woyane government along with the Saudi officals in our slogans and petition. The group rejected our proposed idea. They said they will not allow woyane to be denounced. በሺካጎም እንደኒውዮርኩ ወይም ቶሮንቶው ቡድን ከሳውዲ ጎን ለጎን የወያኔ ስርአትንም ማውገዝ አለብን ብለን ጠየቅን፡፡ ነገር ግን ወያኔ አይነካም በሚል እጅ በእጅ በተሰኘ ቡድን ተዋጥን እንደማለት ነው በጥሬው፡፡

 

ትንታኔ፤ ትችትና ጥቆማ፤

  1. በሳኡዲ ኢትዮጵያዊያን ላይ የደረሰው ግፍ አሰቃቂ ነው፡፡ በርግጥ መጠኑና ቅርጹ ለየት አለ እንጂ፤ የሴቶቻችን መደፈር፤ የኢትዮጵያዊያን በአረብ አገር መገደልና መንገላታት ያለና የነበረ ነው፡፡ ኢትዮጵያ በአሁኑ ቅርጽ እስካለችም ወደፊትም የሚኖር ይመስላል፡፡ ከግፉ ይልቅ ግን፤ ስለግፉ በኢትዮጵያውያን መካከል የታየው ግዙፍ የፖለቲካ አስተሳሰብ ልዩነት በጣም አሳሳቢ ነው፡፡ ጎን ለጎንም፤ ይሄ ወቅት፤ መንግስት ዜጎቹን ለመሰብሰብና ለመጠበቅ አፋጣኝ ምላሽ ለመስጠት ሲሰንፍ፤ በተቃዋሚው በኩል ለዜጎች እንደተለዋጭ መንግስት የሚያስብና የሚሙዋገት ፖለቲካዊ ተቁዋም አለመኖሩ የትግላችንን ሰንካላነትና የተቃወወሞዋችንን ጉዶሎነት ቁልጭ አድርጎ አሳይቶዋል፡፡ ከሀያ ሶስት አመት በሁዋላም፤ ይሄ ነው የምንለው እኛን የሚያሰባስብ አስተማማኝ ተቁዋም ባለመገንባታችን፤ እንደገና ኮሚቴ ወደማቁዋቁዋም ስንራወጥ መመልከት እጅግ አሳዛኝ ነው፡፡ ትግላችን የአድ ሆክ ኮሚቴ ግንባታ ሆነ፡፡
  1. የበለጠ የሚያሳስበው ደግሞ፤ ከዚህ ከሳኡዲ ችግር ጋር በተያያዘ ያቁዋቁዋምነው አለማቀፍ ኮሚቴም፤ አስር ሀያ አመት ከምናደርግበት የትግል ስልት ብዙ ፈቀቅ ያለ አይመስልም፡፡ የኮሚቴው ሙሉ ዝርዝር ባይኖረኝም፤ የሶስቱ ሰዎች ስም እንደሚያሳየው ከሆነ፤ ኮሚቴው ዘመኑን ያልዋጀ፤ የአንድ ብሄር ስብስብ ነው የሚመስለው፡፡ ስብስቡ አለማቀፍም አገርአቀፍም ደረጃውን እንዲጠብቅ አልተደረገም፡፡ ወዳጆቼ ታማኝና አበበን በቅርበት አውቃቸዋለሁ፡፡ በኢትዮጵያዊነት ስሜታቸው ከነሱ የተሣለም የተሻለም አለ ለማለት ይከብዳል፡፡ አቶ ብርሀኑ ዳምጤም እንደሰማሁት ከሆነ ሌሎች የግል ህጸጾች ቢኖሩትም፤ በኢትዮጵያዊነቱ ጥያቄ የሚነሳ አይመስለኝም፡፡ ነገር ግን፤ ቢያንስ ሴቶችና የእስልምና እምነት ተከታዮች መታከል፤ ካሉበትም ደግሞ ግንባር ላይ መቀመጥ ነበረባቸው፡፡  ከታላቁ የኦሮሞ ብሄረሰብም በግልጽ ሚታይ ሰው አለመወከሉ ስህተት ነው፡፡ እንዲህ ያለው እነሱን ያላካተተ ኮሚቴና አካሄድ መብዛቱ ነው ብዙ የኦሮሞ ተቆርቃሪዎችን ሌላ መፈክርና መለያ ይዘው እንዲወጡ የሚጋብዛቸው፡፡ በዚህ ሌሎችን ብሄሮች በማስተናገዱ ረገድ፤ ኢህአዴግ/ሕወሀት ከኛ ብልጥ ነው፡፡
  1. ብዙ በተለምዶ የአንድነት ሀይል ተብሎ በሚጠራው ስብስብ የሚገኙ ሰዎች ይሄንን ብሄርና ሀይማኖትን መሰረት ያደረገ ትችቴ እንደሚጎመዝዛቸው አውቃለሁ፡፡ ጎበዝ፤ ባይሆን ደስ ይለኝ ነበር፡፡ ግን ሆነ፤ ወደድንም ጠላንም ያላፉት 23 አመታት እንደሚያሳዩን፤ ብዜ ግዜ ብሄርን፤ አንዳንዴ ሀይማኖትን መሰረት ያደረገው የኢህአዴግ ፖለቲካዊ ርእዮተ ዓለም  ገዢ ሆኖ ቆይታል፡፡ ሰዎች በብሄር ነቅተዋል፡፡ ሰዎች በሀይማኖትም ነቅተዋል፡፡ ስለዚህ ብንቀበለውም ባንቀበለውም፤ በአደባባይ እንደዚያ ብለን ባናውጅም፤ ይሄንን የሳኡዲን ግፍ ለማለስለስና ለማስቀልበስ የምናቃቁማቸው ተቁዋማትና ስብስቦችም ሁኑ ሌሎች መሰል ፖለቲካዊና ሲቪክ ማህበራቶቻችን፤ በተዘዋዋሪ ይሄንን የሀይማኖትና የብሄር ነባራዊ ሁኔታ ከግምት ያስገቡ መሆን አለባቸው፡፡ እስከአሁን እንደታዘብኩት ከሆነ፤ በኛ በአንድነቱ በኩል ያለምንም ማሻሻያ የድሮውን ኢህአዴግ ከመግባቱ በፊት የነበረውን አሰላለፍ እየደጋገምን ከማንንጸባረቅ ውጪ፤ የኢህአዴግን ርእዮተዓለም የሚያንፉዋቅቅም ይሁን የሚተካ አስተሳብ ማምጣት አልቻልንም፡፡ በዚህ በሰሞኑ ክስተት ውስጥ፤ በትንሹ፤ ለሳኡዲ፤ ከታማኝ ልቁ ሀጂ ነጂብ፤ ከአበበ ይልቅ አባስ አይነ-ግቡ ናቸው፡፡ እንዲህ ያለው ነገር ከፍተኛ አለማቀፍ ዲፕሎማሲያዊ ስራም ስለሚፈልግ፤ ኮሚቴው በቀድሞ ጎምቱ ዲፕሎማቶች ቢጠናከር መልካም ነው፡፡ ኢትዮጵያዊያንን ለማስተባበርና ሳኡዲዎችን ለመጀንጀን የምናቁዋቁመውን ኮሚቴ መለየት ያለብን ይመስለኛል፡፡

ሰልፎቹን ግን ተቀምተናል፡፡

  1. ከዚያ በተረፈ፤ በዚህ በሳኡዲ ግፍ ማግስት በሚደረጉ ሰልፎች ላይ የተወሰኑትን ሰልፎች ተቀምተናል፡፡ ለዚህ ጥሩ ምሳሌ የካናዳ ዋና ከተማ፤ ኦታዋ ነች፡፡ የዛሬ ሶስት አመት ለድህረ ምረቃ ትምህርት ኦታዋ ስገባ፤ የአንጋፋው ፖለቲካ ድርጅት፤ ኢህአፓ አባላት፤ ይሄማ የኛ ግዛት ነው እያሉ እያንዳንዱ የፖለቲካ እንቅስቃሴ በነሱ ፈቃድና ቡራኬ እንዲያልፍ ለማድረግ ይንጎማለሉ ነበር፡፡ ባይሳካላቸውም፡፡ እነሆ የሳኡዲውን ክስተት ተከትሎ በኦታዋ ሰልፍ ሲጠራ ግን፤ የቶሮንቶ ሰልፈኞች በአውቶብስ ተጉዘው ብርታት እስኪሰጡዋቸው ድረስ፤ እነዚያ እኛ ጋር ዘራፍ ይሉ የነበሩት የኢህአፓ ቀናተኞች፤ አንገታቸወንም ይሁን የያዙትን የተቃውሞ መፈክር እንኩዋን ቀና አድርገው ለመሄድ አልደፈሩም፡፡ ኢህአፓዎች ልጆቻቸውን እንኩዋን ሳይተኩ ማርጀታቸው እንዴት እነደማያሳስባቸው ይገርመኛል፡፡ ጎበዝ እያረጀን ነው፡፤ ተተኪ አባላት ሳንወልድ ልናልፍ ነው ብሎ ማን እንደሚነግራቸው እንጃ፡፡ በንጽጽር ግንቦት ሰባት ለወጣቱ የተሻለ መስህብ ቢኖረውም፤ ይሄንን አጋጣሚ እንዋን ተጠቅሞ በኢትዮጵያዊያን ላይ እየደረሰ ያለውን ግፍ ከማውገዝ ባሻገር፤ መደረግ ስለሚገባቸውም ነገሮች ተጨባጭ ነገር መጠቆም አልቻለም፡፡ በውጭ አገር መሪ አጣን፡፡ በዚህ ረገድ በአገር ቤት ያሉት፤ ሰማያዊና አንድነት ፓርቲዎች ይሻላሉ፡፡

እንደ ማጠቃለያ

  1. ጎበዝ ባንዲራውን ተቀምተናል፡፡ አገራችንን ተቀምተናል፡፡ ነጻነታችንን ተቀምተናል፡፡ ሰልፋችን ነበር የቀረን እሱንም ልንቀማ ነው፡፡ ለጊዜው ድነናል፡፡ በዘላቂነት ግን እንጃ፡፡ የኒው ዮርኩ አቶ አለማየሁ እንደጻፈው፤ እነሱ፤ ኢህአዲጎች  መተካካታቸው የምር ነው፡፡ I was hoping that the Woyanne and its supporter’s children grew up in melting pot cities such as, Addis and free of hatred. It appears they are here to make us shut our mouth and take their parent’s torch:: ወያኔና ደጋገፊዎቹ እንደአዲስ አበባ ባሉ ሰፊ ከተሞች በማደጋቸው ከጥላቻ ነጻ ናቸው ብዬ አስብ ነበር፡፡ ይሁን እንጂ፤ የወላጆቻቸውን ችቦ ተቀብለው፤ እዚህም አፋችንን ሊያዘጉን ይፈልጋሉ፡፡ የህወሀት ልጆች ዘመናዊ ትምህርት በአውሮፓና አሜሪካ ቢማሩም፤ ባህላዊውን ፖለቲካም በሚገባ እየሸመደዱት ነው፡፡ በርግጥም በተወሰነ መልኩ የመፈክሮቻችንን ቅኝቶች ለውጠዋቸዋል፡፡ በዚህ ሳምንት የቶሮንቶ የኢትዮጵያ ማህበር ባዘጋጀው ሰልፍ ላይ፤ አመራሩ መፈክሮቹና ንግግሮቹ ፖለቲካዊ እንዳሆይኑ ለማድረግ ያደርግ የነበረውን ጥንቃቄ ለተመለከተ፤ በርግጥም ኢህአዴግ/ሕወሀት አካሄዳችንን ምን ያህል እንደሸበው ያሳያል፡፡
  1. በዚህ የሳኡዲ ክስተት የተረዳሁት ነገር ቢኖር ከዚህ ቀደም በተካንበት ነገር ስንኩዋን መቀደማችንን ነው፡፡ በአንዳንዶቹ እኔ በቅርበት በታዘብካቸው ሰልፎች ያየሁት ነገር ቢኖር፤ ሰልፎቹ የተዘጋጁት ወይንም የመጀመሪያውን ተነሳሽነት የወሰዱት፤ አንድም የመንግስት ደጋፊዎች ናቸው፤ ወይንም ከጀርባቸው የመንግስት ደጋፊዎች የተደበቁባቸው ፖለቲካን እንደእሳት የሚፈሩ ገለልተኛ የተሰኙ ሰዎች ናቸው፡፡ ይህ ክስተት ድክመታችን የተጋለጠበት፤ ገመናችን የታየበት፤ እኛ እያረጅን ልጆቻችንን ሳንተካ፤ ኢህአዴግ/ሕወሀቶች ግን ልጆቻቸውን ሲተኩ የተመለከትንበት ክስተት ነው፡፡ ኢህአዴግ የደንቆሮዎች ስብስብ መሆኑ እንጂ፤ ይሄ እንኩዋን እርቅ ለመፍጠር መልካም አጋጣሚ ነበር፡፡ ይሄ አንድነት አንድነት የሚባል ነገር ባይመቸንም፤ በተቃዋሚውም ዘንድ የኢህአዴግን ድንቁርና ትንሽ ስለምንጋራ እንጂ፤ ለአንድነት መልካም አጋጣሚ ነበር፡፡ አልሆነም፡፡ ልዩነታችን ግን፤ ቢያንስ አነሱ አውራ-ፓርቲ አላቸው፡፡ እኛ ግን አውራም፤ አውራ ፓርቲም የለንም፡፡ ጎበዝ፤ 23ኛ ፓርቲ አያስፈልገንም፡፡ አንድ አሸናፊ እነጂ፡፡

 

ተክለሚካኤል አበበ ሳኅለማሪም፤ ቶሮንቶ፤ ካናዳ፤ የህዳር ሚካኤል ሳምንት፡ 2006/2013

Pen

↧

የሳምንቱ የአብርሃ ደስታ በፌስቡክ ላይ የተለቀቁ ምርጥ ጽህፎች

$
0
0

ትናንትና ዛሬ!
——————–

Abrham Destaበሑመራ ከተማ ከሚገኘው አንድ ባንክ በሚልዮን የሚቆጠር ገንዘብ ለማጭበርበር ወይ ለመዝረፍ ሞክረዋል ወይ ወስደዋል ተብለው የተጠረጠሩ ሰዎች ለማእከላዊ ምርመራ ወደ አዲስ አበባ መወሰዳቸው ሰማሁ። የሑመራና አከባቢው ፖሊስ እንደሚለው ባንክ የዘረፉ ወይ ለመዝረፍ የሞከሩ ግለሰቦች የዴ.ም.ህ.ት ታጋዮች ናቸው (ይህ በመንግስት አካላት ለአከባቢው ህዝብ የተነገረ ነው)።

ከሑመራው ጉዳይ የተያያዘ ነው መሰለኝ እዚሁ መቐለም ባንኮችና የመንግስት መስራቤቶች (በተለይ የህወሓት ቢሮዎች) ሃያ አራት ሰዓት በፀጥታ አካላት እየተጠበቁ ነው። ከመከላከያ፣ ፖሊስና ደህንነት የተውጣጣ አንድ ግብረሃይል (Command Post) የመንግስት ተቋማትን (በተለይ ባንኮች) በተለየ ሁኔታ ጥበቃና ክትትል እያደረገ ይገኛል። ግብረሃይሉ የሚያግዙ አዲስ አበባ የሰለጠኑ ወደ አምስት መቶ የሚሆኑ ወጣት ሲቪል ፖሊሶች (ጀሮ ጠቢ) በዚሁ ወር በመቐለ ከተማ ተሰማርተዋል።

ፀጥታ ማስከበር መሞከራቸው ጥሩ ነው። ስለ ባንክ ዘረፋ ጉዳይ ስሰማ ግን አንድ ነገር ትዝ አለኝ። ድሮ በደርግ ግዜ የህወሓት ታጋዮች በአክሱም ባንክ ሲዘርፉ የጀግና አቀባበል ተደርጎላቸው ነበር። ህወሓቶች ስልጣን ከያዙ በኋላም ባንክን የዘረፉ ግለሰቦች ጀግኖች ተብለው እነሱን ለማወደስ ፊልም ተሰርቶላቸዋል። ላከናወኑት የዝርፍያ ተግባር ለማሞካሸት ቁልፍ ስልጣን ተሰጣቸው። እስካሁንም የኢትዮጵያ ገዢዎች ሁነው እያገለገሉ ነው።

ድሮ ባንክ የዘረፈ ተሸለመ፤ አሁን ባንክ የዘረፈ ወንጀለኛ ነው። ባንክ መዝረፍ አንድ ተግባር ነው፤ አንድም ወንጀል ነው አልያም ደግሞ ጀግንነት ነው። አሁን በሑመራ ባንክ ለመዝረፍ ሞክረዋል ተብለው የተጠረጠሩ ግለሰቦች (አድርገውት ከሆነ) ወንጀለኞች (ጥፋተኞች) ተብለው እንደሚፈረዱ ሳይታለም የተፈታ ነው።

በሕግ መሰረት ባንክ መዝረፍ ወንጀል ነው። ድሮ ህወሓቶች ባንክ ሲዘርፉም ተግባሩ ወንጀል ነበር። ግን ህወሓቶች ለዘረፉት ነገር ተጠያቂ አልሆኑም። እንዳውም ለነሱ ባንክ መዝረፋቸው የጀግንነት ተግባር ነበር። ራሳቸው ባንክ ዘርፈው የተሸለሙ ሰዎች አሁን ተመሳሳይ ተግባር ለፈፀሙ (ባንክ ለዘረፉ) ግለሰቦች የጥፋተኝነት ዉሳኔ ይሰጣሉ። ራሳቸው ባንክ ሲዘርፉ ጀግንነት ነው፤ ሌሎች ባንክ ሲዘርፉ ግን ወንጀል ነው።

ግን እንዴት ሆነ? በደርግ ግዜ ባንክ መዝረፍ ወንጀል ነበር። ግን ወንጀለኛ የሚኮነው ስትሸነፍ ነው። ህወሓቶች ባንክ ሲዘርፉ በደርግ ወታደሮች ቢያዙ ኖሮ ወንጀሎች ተብለው በህዝብ ፊት ይረሸኑ ነበር። ዉምብድና በራሱ ሕገወጥ ነበር። ለህወሓቶች ግን ዉምብድና ጀግንነት ነበር። አሁን ውንብድና ይሁን ባንክ መዝረፍ ወንጀል ነው። ህወሓቶች ግን ራሳቸው እንደ ጥሩ ነገር ቆጥረው ሲያደርጉት የነበረውን ተግባር እንዴት አሁን ሕገወጥ አደረጉት?

አዎ! ህወሓቶች ዉምብድና ሲሰሩ (ለምሳሌ ባንክ ሲዘርፉ) ወንጀለኞች ተብለው ከመያዝ ይልቅ ጀግኖች ተብለው የተሸለሙበት ምክንያት ስላሸነፉ ብቻ ነው። ህወሓቶች አሸንፈው ስልጣኑ ስለተቆጣጠሩት የሰሩት ጥፋት ሁሉ ወንጀል ሳይሆን ጀግንነት ሆነ። ህወሓቶች ቢሸነፉ ኖሮ ግን ተግባራቸው ጀግነንት ሳይሆን ዉርዴት ይሆን ነበር። ስለዚህ ወንጀለኝነት/ጀግንነት ከመሸነፍ/ማሸነፍ ግንኙነት አለው።

በቃ ከተሸነፍክ ወንጀለኛ ትሆናለህ። ካሸነክፍ ደግሞ ጥፋትህ ሁሉ እንደ ጀብድነት ይቆጠርልሃል። በሰው አገዛዝ ትልቁ ወንጀል መሸነፍ ነው። አንድ ወጣት እንውሰድ። ተርቧልና ከባንክ አንድ ሺ ብር ሰርቆ ጠፍቷል። በፖሊስ ከተያዘ በስርቅ ወንጀል ተከሶ ወህኒ ይወርዳል። ያ ልጅ አቅም አግኝቶ፣ የራሱ ፖሊስና ወታደር ይዞ ገዢውን ፓርቲ አሸንፎ ስልጣን ቢቆጣጠር ኖሮ ግን አንድ ሺ ብር ቀርቶ አንድ ሚልዮን ብር ቢያጭበረብር የማይጠየቅበት ሰፊ ዕድል አለው።

በመቐለ ከተማ አንድ በካድሬዎች የሚናፈስ ወሬ አለ። ከወራት በፊት በፊትዋ አስገራሚ ፅሑፍ የነበራት አንድ ዕብድ መሳይ ለማኝ ነበረች። አሁን አትታይም። አሁን እንደምንሰማው ከሆነ (ትክክል ስለመሆኑ እርግጠኛ አይደለሁም፣ ግን ‘ግርማይ ገብሩ’ የተባለ ጋዜጠኛም ስለሷ መፃፉ አስታውሳለሁ) ለማኟ በፀጥታ ሃይሎች ቁጥጥር ስር ዉላለች። ምክንያት: የዴምህት ሰላይ ሆና በመገኘቷ የሚል ነው።

ይህ የለማኟ ወሬ የድሮ የህወሓት ታሪክ ያስታውሰኛል። ህወሓቶች አንድ ጓዳቸው በውምብድና ወንጅል ተጠርጥሮ በደርጎች ተይዞ ይታሰራል። ጓዳቸውን ለማስፈታት የታሰረበት ቦታና ሌላ ተያያዥ መረጃዎች ማግኘት አስፈላጊ ነበርና ሰላይ ወደ ቦታው ላኩ። የተላከው ሰላይ ስዩም መስፍን ነበር። ስዩም ዕብድ ሁኖ ነበር የሚሰልለው። ዕብድ መስሎ ለመሰለል የተፈለገው የመንግስት የፀጥታ ሃይሎችን ለመሸወድ ነበር።

ይህን ጉዳይ (ዕብድ መስሎ መሰለይ) በህወሓቶች እንደ ጥሩ ስትራተጂ ተወስዶ ፊልም ተሰርቶበታል (‘ሙሴ’ ፊልም ይመለከቱ)። ብዙ ነገር ተብሎለታል። ስዩም ዕብድ መስሎ መሰለይ በመቻሉ ቆራጥና ጀግና ተብሏል። ምክንያቱም ህወሓቶች አሸንፈዋል። እንዳሁኗ ስዩም መስፍን በመንግስት (በደርግ) ፀጥታ ሃይሎች ቢያዝ ኖሮስ? ወንጀለኛ ተብሎ ይሰቃይ ነበር። ቶርቸር ይደረግ ነበር።

ያሁኗስ (አሁን የተያዘች ለማኝ)? በጠላት እጅ ወድቃለች። ስለዚህ ትሰቃያለች። ምክንያቱም ወንጀለኛ ናት። ምክንያቱም ለግዜው አላሸነፈችም። ምናልባት (እንደሚባለው የዴምህት ሰላይ ናት ብለን እናስብና) ዴምህቶች አሸንፈው ስልጣን ከተቆጣጠሩ ልጅቷ ‘ጀግና’ ተብላ ፊልምና ሐውልት ይሰራላት ይሆናል። አሁን በህወሓቶች ከተገደለችም ልክ እንደነ ‘አሞራ’ና ‘ቀሺ ገብሩ’ ዘጋቢ ፊልም ተዘጋጅቶላት ታሪኳ ይተረክልን ይሆናል። ዴምህቶች ከተሸነፉ ግን ወንጀለኛ እንደተባለች ትቀራለች። ስሟም አይነሳም። ህወሓቶች ባያሸንፉ ኖሮ ስለ አሞራና ቀሺ ገብሩ ምንም ነገር አንሰማም ነበር። ተራ ወንበዴዎች እንደሆኑ ይቀሩ ነበር። ልጅቷ ሰላይ ናት የሚል ግምት የለኝም ምክንያቱም ሰላይ ብትሆን ኖሮ ቀልብ (ትኩረት) የሚስብ ነገር (የፊትዋ ፅሑፍ) አታረግም ነገር። ሰላይ ቀልብ የሚስብ ነገር ማድረግ የለበትም።

ህወሓቶች ‘ስዩም መስፍን ዕብድ መስሎ ለመሰለል የፈለገው ለዓላማ ነበር’ ይሉን ይሆናል። ዴምህቶችም ‘ለማኟ ዕብድ መስላ ለመሰለል የሞከረችው ዓላማ ስለሆነ ነው’ ሳይሉን አይቀሩም። ነጥቡ ግን ‘እርስበርሳችን መሰለል፣ መገዳደል ለምን አስፈለገ?’ የሚል ነው።

ጀግኖችን እናደንቃለን። ጀግና መሆን ግን ያስፈራናል። ጀግና ለመሆን ፈተናን ፊትለፊት መጋፈጥ ይኖርብናል። ከፈተና በመሸሽ ጀግንነት አይገኝም። ፈተና የጀግንነት መንገድ ነው። ጀግናን ማድነቅ ጀግና አያደርግም። ጀግና የሚያደርገን ፈተና ነው። ላብዛኛው አስፈሪ የሆነ ፈተና ለኛ የጀግንነት መለኪያችን ነው። ጀግኖችን የምናደንቅ ከሆነ ለምን ራሳችን ጀግና ለመሆን አንጥርም?

ዞሮዞሮ በሰው አገዛዝ ስርዓት ሕግ የሚወጣው ገዢው እንዲገለገልበት እንጂ ፍትሕ ለማስፈን አይደለም። ገዢዎች ህዝብን ለመጨቆን እንዲያገለግላቸው የራሳቸው ሕግ ያወጣሉ። ሕጉ እነሱን አይመለከትም። ገዢዎቹ ከሕግ በላይ ናቸውና። ገዢዎች ሕግ የሚያወጡት ተፎካካሪዎቻቸውን ለመቅጣት ነው።

አሁን የምንፈለገው የገዢዎች የራስ ሕግ ሳይሆን የህዝብ ሕግ ነው። በህዝብ ሕግ ሁሉም ሰው (ገዢም ተገዢም) እኩል ነው። የሕግ የበላይነት ይኖራል። ሰው በወንጀል የሚጠየቀው ጥፋት ሲሰራ እንጂ ሲሸነፍ ብቻ አይደለም። የሕግ የበላይነት ሲኖር ሁሉም (አሸናፊውም ተሸናፊውም) ከሕግ በታች ይሆናል፣ በሕግ ይጠየቃል። ገዢው ሰው ሳይሆን ሕጉ ይሆናል።

አሁን የስርዓት ለውጥ ያስፈልጋል። ሰዎች ሳይገድሉና ሳይገደሉ የፖለቲካ ስርዓት ለውጥ የምናመጣበት መንገድ ማመቻቸት ይኖርብናል። ያሁኑ ባለስልጣናትም የማይሰደዱበት (የማይገደሉበት)፣ ከሀገር ዉጭ ያሉ (የሃይል መንገድ የመረጡ ሃይሎችም) በሰላም ወደ ሀገራቸው የሚገቡበት ሁኔታ የሚፈጠርበት ሀገራዊ መግባባትና ዕርቅ እንፈልጋለን። ስልጣን ለመያዝ ይሁን ስልጣን ለመልቀቅ የሞት ስጋት መኖር የለበትም።

ሰው ሳይሰደድና ሳያሳድድ፣ ሳይገድልና ሳይገደል የስልጣን ሽግግር የሚደረግበት የፖለቲካ መድረክ እንጠብቃለን። ስልጣን ለመያዝ ወይ በስልጣን ለመቆየት ደም መፋሰስ ይቁም።

 

 

አንዱአለም አራጌና አስተያየቶች!
———————————–

ትናንት እንዲህ ፅፌ ነበር:

“ከትግራይ ሰዎች ባሰባሰብኩት መረጃ መሰረት ባሁኑ ሰዓት ክብርና አድናቆት የተቸረው የተቃዋሚ ፖለቲካ መሪ አንዱአለም አራጌ ነው። (በትግራይ ሰዎች የሚወደድ ተቃዋሚ ፖለቲከኛ: አንዱአለም)!”

ከተሰጡኝ አስተያየቶች በመነሳት አንድ ነገር ተገነዘብኩ፤ አንድም እኔ አማርኛ አልችልም (የፈለኩትን አልገለፅኩም) አልያም ደግሞ የትግራይ አንባቢዎቼ የአማርኛ ቋንቋ ችግር አለባቸው።

እኔ የፃፍኩት “ከትግራይ ሰዎች” የሚል ነው። እኔ እንደሚገባኝ “ከትግራይ ሰዎች” ማለት ትግርኛ የሚናገሩ ግለሰቦች ማለት እንጂ የትግራይ ህዝብ ወይም የመቀሌ ወይ የሌላ አከባቢ ኗሪዎች ማለት አይደለም። አንድ ሰውም ትግርኛ ተናጋሪ ከሆነ የትግራይ ሰው ነው፤ የትግራይ ህዝብ ግን አይወክልም። ስለዚህ “ከትግራይ ሰዎች” ብዬ ስል ያናገርኳቸው ሰዎች የትግራይ (ትግርኛ ተናጋሪ) ናቸው ለማለት ነው።

ሌላው ችግር የፈጠረው ሐረግ “ባሰባሰብኩት መረጃ” የሚል ነው። እዚህ ላይ መረጃ መሰብሰብና ጥናት ማካሄድ ይለያያሉ። መረጃ ሰበሰብኩ እንጂ ጥናት አላካሄድኩም። መረጃ ያሰባሰብኩት Informal በሆነ መንገድ ነው። ስለዚህ ለትግራይ ህዝብ ኮሽኔር (questionnaire) በመበተን የተሰበሰበ መረጃ አይደለም።

ሌላው ደግሞ “ከተቃዋሚ የፖለቲካ መሪዎች ነው” እንጂ ከአጠቃላይ ፖለቲከኞች አይደለም። አሁንም የትግራይ ሰዎች (ትግርኛ ተናጋሪ) እንደነገሩኝ ከሆነ ከተቃዋሚ ፖለቲካ መሪዎች ተወዳጁ አንዱኣለም ነው።

መረጃ የሰጡኝ ሰዎች (አንደኛ) የትግራይ ሰዎች ናቸው፣ የሌሎች ክልሎች ግምት ዉስጥ አላስገባሁም። (ሁለተኛ) መረጃ የተቀበልኳቸው ሰዎች አንዱኣለምን በቅርበት የሚያውቁ ወይም በቂ መረጃ ያላቸው ናቸው። (ሦስተኛ) መረጃው የተሰበሰበው ስርዓት ባለው መደበኛ አሰራር አይደለም (Informal ነው)። በስተመጨረሻ አከባቢ ግን ሆን ብዬ ስለሱ መረጃ እያሰባሰብኩ ነበረ። (አራተኛ) መረጃ የሰጡ ሰዎች በፖለቲካ ተሳትፎ ያላቸው ብቻ ናቸው (ከአምስት ሰዎች ዉጭ)።

በዚሁ መሰረት ከአርባ ሦስት ሰዎች (እኔ አርባ አራተኛ ነኝ) የሰበሰብኩት መረጃ ነው። እነኚህ ሁሉ ትግርኛ ተናጋሪ (የትግራይ ሰዎች) ብቻ ናቸው። አስራዘጠኙ የዓረና ትግራይ ፓርቲ አባላትና ደጋፊዎች፣ አስራአንድ የህወሓት አባላት (አብዛኞቹ የደህንነት ሰዎች)፣ ሦስት የአንድነት ፓርቲ አባላት፣ አምስት የፖለቲካ ፓርቲ አባላት ያልሆኑ፣ ሁለት የተቃዋሚ ፓርቲ አባላት የነበሩ (አሁን ግን ያልሆኑ)፣ ሌሎች ሦስት ሰዎች ደግሞ የፖለቲካ አቋማቸው በግልፅ ማወቅ አልቻልኩም።

ከነዚህ ሰዎች አብዛኞቹ አንዱኣለም አራጌን ያደነቁበት ምክንያት (አንድ) በሚሰጠው በሳል ሓሳብ፣ (ሁለት) የጥላቻ ፖለቲካ ስለማያራምድ። በብዙዎቹ አገላለፅ አንዱአለም ምንም ዓይነት የብሄር (የጥላቻ) ፖለቲካ አያራምድም። በኢህአዴግ የታሰረውም በፖለቲካ ብቃቱ ምክንያት ገዢውን ፓርቲ ስላሰጋ ነው ሊሆን የሚችለው ብለዋል። ከሰዎቹ ስድስቱ ግን ስለ አንዱኣለም መጥፎም ጥሩም አልተናገሩም።

በዚህ መሰረት ነው አንዱኣለም አራጌ በትግራይ ሰዎች (ትግርኛ ተናጋሪ ግለሰቦች) ተወዳጁ የተቃውሞ ፖለቲካ መሪ ነው ብዬ ለመፃፍ የተገደድኩት። አሁንም ልብ በሉ ከተቃዋሚ ፖለቲከኞች ነው።

እኔም ስለ አንዱኣለም አራጌ መረጃ ያገኘሁት ከነዚህ ሰዎች ነው።

 

 

 

↧
↧

ዶክተር ያዕቆብ ሀይለማርያም የአንዱአለም አራጌ መፅሀፍ ሲመረቅ ያስተላለፉት መልዕክት (ቪድወ )

$
0
0
↧

የትምህርት ተቌማት የእውቀት ወይስ የፖለቲካ ሜዳ!?

$
0
0

ከቅዱስ ዮሃንስ

 

higher educationትምህርት ዜጎችን ሁለንተናዊ በሆነ መልኩ በመቅረጽ ለራሳቸው፣ ለማህበረሰባቸውና ለሃገራቸው ጠቃሚ ዜጋ እንዲሆኑ የሚያግዝ የእውቀት ማሸጋገርያ ስልት ነው፡፡ ዛሬ በስልጣኔ የገሰገሱ የአለም ሀገራት የዕድገታቸው ዋነኛ መነሻ ትምህርት ምርምርና የቴክኖሎጂ ሽግግር ነው። ግብርና፣ ኢንዱስትሪ፣ የአገልግሎት ፓኬጅም ሆነ ሌሎች የኢኮኖሚ ዘርፎች በዘመናዊ አኳሃን እንዲመነደጉ ከተፈለገ በተግባር የታገዘ፣ ፈጠራና ክህሎትን የሚያዳብር ጥራት ያለው ትምህርት እጅግ ወሳኝ ነው፡፡

የትምህርት መሰረት በኢትዮጵያ ውስጥ መጣል ከጀመረ ከመቶ ዓመታት በላይ የተቆጠረ ሲሆን ከሁለተኛው አለም ጦርነት በፊት ትምህርት የሚሰጠው በመንግስትና በሃይማኖት ተቋማት ዙርያ ለአስተዳደራዊ ክህሎት፣ ለቀኖናና ለሃይማኖት እውቀት ሲባል እንደነበረ ጥናቶች ይገልጻሉ፡፡ ከሁለተኛው ዓለም ጦርነት በኋላ የአፄ ሃይለ ስላሴ ስርዓት ዘመናዊ ትምህርትን በተደራጀ መልኩ በትምህርት ቤቶች ውስጥ እንዲሰጡ ሁኔታዎችን ያመቻቸ ቢሆንም የትምህርት ቤቶች እድገት ከማህበረሰቡም ሆነ ከሃይማኖት ተቋማት በገጠመው ተጽእኖ ምክንያት የመስፋፋቱ እድል አዝጋሚ ሆኖ ቆይቷል፡፡ በደርግ ወቅቱም ቢሆን የነበረው አጣዳፊ ጉዳይ አብዮቱ በመሆኑ በመማርና ማስተማር ላይ የነበሩትን መምህራንና ተማሪዎች በነቂስ አሰልፎ አብዮቱን ለማስተዋወቅ በሚል ሰበብ ወደ እድገት በሕብረት የዕውቅትና የስራ ዘመቻ አዘመተ፡፡ ከብዙ ጥረት በኋላ እራሱን በጥቂቱም ቢሆን ማጎልበት የጀመረው የትምህርት ስርዓት ከባድ ፈተና ውስጥ ወደቀ፡፡ በማያባራ ዘመቻ፣ ግድያ፣ አፈናና ጦርነት ተተብትቦ እራሱን ፋታ የተነሳው ደርግ፤ በቂ ትምህርት ቤቶችን ለመገንባትና መምህራንን ለማብቃት ጊዜ አልነበረውም፡፡ በዚህም ምክንያት መምህር አልነበሩም፡፡ ትምህርት ቤቶችና ለመማር ማስተማር ሂደቱ በሚያስፈልጉ ግብአቶችና ቁሳቁሶች አልተሟሉም፡፡ የትምህርት ስርዓቱ በአጠቃላይ እርቃኑን እንደቀረ ነበር፡፡ ይህንንም ተከትሎ የኢትዮጵያ የትምህርት ስርዓተ ውድቀት አንድ ተብሎ ተጀመረ፡፡

 

የኢትዮጵያን የትምህርት ስርዓት ተብትበውና ቀስፈው የያዙት ችግሮች ከደርግ ጋር ተዳብለው ስር እየሰደዱ ቆይተው፣ ዛሬም በኢህአዴግ ውስጥ በመሸጋገር ማጣፊያ እንዳጠራቸው ቀጥለዋል ፡፡ የመማር ማስተማር ሂደቱ በደርግ ስርዓት የለከፈው የማጥራት ሳይሆን በማብዛት፣ በማዳረስ ላይ የመተማመን በሽታ ዛሬም ወያኔን ቀስፎ እንደያዘው ይገኛል፡፡ ትምህርትን ለሁሉም ዜጐች በስፋት የማድረስ ተልዕኮን እንደያዘ የሚያስበው ወያኔ፤ የትምህርቱን የጥራት ደረጃ ለዚህ ግቡ ሲል እየጨፈለቀው ስለመሆኑ ብዙ ጥናቶች አረጋግጠዋል። ሀገሪቱ ካስቀመጠችው አነስተኛ ማለፊያ ነጥብ እጅግ ያነሰ ውጤት የሚያመጡ ተማሪዎች ከመጀመሪያ እስከ ሁለተኛ ደረጃ ባሉት የትምህርት እርከኖች ቁጥራቸው እየበዛ መምጣቱ ሳያንስ፤ ወደ መሰናዶ ትምህርት የገቡት በሙሉ ለሙሉ በሚባል መልኩ ወደ ዩኒቨርስቲ የሚገቡበት አሳፋሪ ሁኔታ ተፈጥሯል። ለየትምህርት ክፍሎቹ በማይመጥኑ መምህራን መማር፣ በአነስተኛ ደረጃ መሟላት ይገባቸው የነበሩት የትምህርት መሳሪያዎች እጦት አልፎም የአካዳሚያዊ ነፃነት በፖለቲካዊው ስርዓት በጥልቁ መጣስ፤ የኢትዮጵያ ትምህርት ተቋማት መሰረታዊ መለዮ ሆኗል። የዚህ ፅሁፍ ዋና ትኩረት የትምህርት ስርአቱን ቀስፈው የያዙት ችግሮችን አንድ በአንድ ነቅሶ ማሳየትና መዳሰስ ሳይሆን፤ ለስርአቱ ውድቀት በተለይም ለጥራቱ ዝቅጠት ግንባር ቀደም መንስኤዏች ተብለው ከሚፈረጁት መካከል ትምህርትን ለፖለቲካ ፍጆታ መጠቀም ላይ ትኩረት ያደርጋል።

 

የወያኔ መንግስት ትምህርትና የትምህርት ተቋማትን ለፖለቲካ ፍጆታ በመጠቀሙ ላይ ይገኛል፡፡ በአሁኑ ወቅት የመምህራን አመራረጥ በተለይም ለከፍተኛ ትምህርት አስተማሪነት የሚታጩ መምህራን የመለኪያው ዋና መስፈርት የፖለቲካ አቋም መሆኑን መመልከት ይቻላል። ወያኔ በዘረጋው የትምህርት ዘርፍ ከሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት ጀምሮ እስከ ከፍተኛ ተቋማት ድረስ መምህራን የሚመለመሉት በፖለቲካ መስፈርት ነው። በነዚህ የትምህርት ደረጃዎች ችግሮች በቀጥታ ከትምህርት ጋር የተያያዙ መሆናቸው እየቀረ ፖለቲካዊ ይዘት እየተጎናፀፉ መጥተዋል፡፡ የወያኔ የካድሬ እንቁላል መጣል እና የረጅም ጊዜ አሕዳዊ አገዛዝ ፍላጎት የራስ መከላከል ሥራዎች በይፋ ይጀመራሉ፡፡ ባለፈው በደርግ ስርዓት ውስጥም ትምህርቱ ከሶሻሊዝም ርዕዩተ ዓለም ውጪ አልነበረም። አሁንም ቢሆን ትምህርትና ተቋማት በፖለቲካውና በአብዮታዊ ዴሞክራሲ ርዕዮተ -ዓለም የተቃኙ ናቸው። ከዚህም በላይ መንግስት ዩኒቨርስቲ መክፈትን እንደ ፖለቲካዊ አፍ የማዘጊያ ስልት ተጠቅሞ የፖለቲካ ድጋፍና ታማኝነትን እንደማግኛ መሳሪያ እየተገለገለበት ነው፡፡ ዛሬ በሃገራችን ቁጥራቸው በርከት ያሉ ዩኒቨርስቲዎች ተገንብተው አገልግሎት በመስጠት ላይ መገኘታቸው እሰይ የሚያስብል ቢሆንም እጅግ አሳዛኙ ነገር ግን ሁሉም ተቋማት በፖለቲካ ተተብትበው የእውቀት አምባ መሆናቸው ቀርቶ የካድሬ መፈልፈያ ተቋማት መሆናቸው ነው። ይህም የትምህርት ጥራቱን እንዲያሽቆለቁል አድርጐታል።

 

ወያኔ በዩኒቨርስቲዎች እና በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ውስጥ ያሉ ተማሪዎች በነጻነት እንዲያስቡ አይፈለግም፤ አይፈቀድምም፡፡ እንኳን ተማሪዎቹ ይቅርና መምህራኑ ጭምር በነጻነት የሚያስተምሩትን ለመምረጥ አይደፍሩም፡፡ በንድፈ-ሐሳብ ደረጃ ለተማሪዎቻቸው የሚያስተላልፉትን እውቀት ሀገሪቷ ላይ ካለ ነባራዊ ሁኔታ አንጻር ተንትኖ ለማስረዳት የሚደፍሩት ጥቂቶች ብቻ ናቸው፡፡ ክፍል ውስጥ ለሚያስተምሩትም

ሆነ ለሚናገሩት ነገር ልክ በቤተ ክህነት ውስጥ የአምላክን ቃል እንደሚሰብክ ሰባኪ ጥንቃቄን ማድረግ ግድ ይላቸዋል። ይህ ሁሉ የሚሆነው የተዘረጋውን አስጨናቂ የአምባገነን ስርአት ከመፍራት፤ የተናገሩት ነገር ገዥው ፓርቲን የሚነቅፍ (የማይደግፍ) ከሆነ ያለአግባብ ስም ተለጥፎባቸው የእንጅራ ገመዳቸውን ስለሚበጠስ ነው። በለፈለፉ ባፍ ይጠፉ ይባል የለ። ከክፍል ውጪም በተቋማቱ አመራሮች ለሚፈፀሙ የአሰራር ስህተቶች እና በደሎች ለመተቸት እምብዛም ፈቃደኛ አይደሉም፡፡ ምክንያቱም አመራር ተብለው የሚሾሙት የትምህርት ተቌማት ባስልጣናት የተሻለ እውቀትና ልምድ ያላቸው ሰዎች ሳይሆኑ የመንግስት ቀኝ እጅ በመሆን የሚያገለግሉት የወያኔ ግልገል ካድሬ ናቸው። እነዚህ አካላት በሚያስተዳድሩት መምህራን ላይ ኢፍትሃዊ እርምጃ ቢወስዱም ማንም ሃይ ባይ የላቸውም።

 

ተማሪዎች በአብዛኛው ለትምህርታቸው የሚሰጡት ትኩረት እና ውጤታቸው ምንም አያስጨንቃቸው፤ ደንታቸውም አደለምም ለማለት ያስደፍራል። ከዚህ ይልቅ የወጣቶች ሊግ እና ማንኛውንም የመሪው ፓርቲ ተደራሽነት የሚያሳድጉ/የሚያጠናክሩ ሥራዎች ላይ ንቁ ተሳታፊ በመሆን ታትረው ይሰራሉ። ይህም በጓደኞቻቸው ላይ የበላይነትን እንዲያገኙ ከማድረጉም በላይ ተሰሚነትን በትምህርት ቤት ኃላፊዎች ያስገኝላቸዋል፤ ከበድ ሲልም የንግድ እና የፖለቲካ ሥራ እንዲያገኙ ይመቻችላቸዋል፡፡ ይህ በትምህርት ዘርፍ ላይ የተዘረጋው ስርዓት ለተማሪዎች የሚያስተላልፈው መልእክት ግልፅ ነው፡፡ በትምህርት ተግቶ እውቀት ሸምቶ ሀገሪቷን ለመጥቀም ከመታተር ይልቅ ርካሽ የፖለቲካ ተወዳጅነት ማግኘት የስኬት መንገድ አቋራጭ መሆኑን ነው፡፡ ለትምህርት ትኩረት መስጠት ያለውን ጥቅም ተረድተው ይሻለኛል ብለው የሕይወት መስመራቸውን የሚያስተካክሉት ተማሪዎች ቁጥር እጅግ በሚያሳዝን ሁኔታ አሽቆልቁሏል።

 

በአሁኑ ወቅት ወያኔ በመላ ሀገሪቱ ውስጥ ከሚገኙ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ከሚማሩት ውስጥ 85% የሚሆኑ አባላት እንዳሉት እና በእያንዳንዱ የትምህርት ክፍሎች ውስጥ ህዋስ እንደዘረጋ ይገልፃል፡፡ እንግዲህ ይህ ፐርሰንት በመመልከት አብዛኞቹ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች የስርዓቱ አካል እና አስፈጻሚ እንደሆኑ መናገር ይቻላል፡፡ እጅግ አሳዛኙ እውነታው ግን እነዚህ ሁሉ አባላት ወደ ድርጅቱ የተቀላቀሉት በፍላጐት ሳይሆን በግዳጅ ብሎም በሃገሪቱ የተዘረጋው አላፈናፍን ያለው አስጨናቂው ስርአት የሚያስከትልባቸውን የከፋ መዘዝ ለመሸሽ ከመፈለግ መሆኑ ነው። ከዚህ ጋር ተያይዞ በዩንቨርስቲዎች ውስጥ እየታየ ያለው አዲስ ገፅታ፤ የተማሪዎች ጊዜያቸውን በህዋስ ውይይት እና ግምገማ ማዋላቸው፣ ከአባላት ሁሉ ልቆ ለመታየት የሚደረግ ጥረት፣ ከትምህርት ውጤታቸው ይልቅ፤ በአባልነታቸው ወደሚሰጣቸውን ነጥብ መጨነቅና አብዝቶ ማተኮር፣ ሲብስም የትምህርት ጊዜያቸውን መሉ በሙሉ ለማለት በሚያስደፍር መልኩ ለፓርቲ ተግባራት በማዋል የመጡበትን ዋነኛ የትምህርት አላማ በመሸሽ፤ ብቁ የካድሬ ምሩቃን ሆነው ለመውጣት ወ.ዘ.ተ መሽቀዳደም የተማሪዎች መገለጫዎች ናቸው፡፡ ይህም የተሻለ ስራ እንዲያገኙ ያግዛቸዋል፤ በተቃራኒው ይህንን የሚሸሹ ምሩቃን ለስራ ማጣት እና ለከፋ ችግር እየተጋለጡ ይገኛሉ።

 

በመጨረሻም መንግስት ትምህርትና ተቋማቱን የፖለቲካ ሜዳ ከማድረግ መታቀብ አለበት፤ ከካድሬዎችም ነፃ ማድረግና የእውቀት አምባ ብቻ ሆነው መቀጠል ይኖርባቸዋል። በዘርፉ ያለው የፖለቲካ ጣልቃ ገብነት መስተካከል እንደሚገባው፣ ተማሪዎችና መምህራኖች አካዳሚክ ነፃነት ማግኘት እንዳለባቸው፣ ተቋማቱ ዕውቀት የሚገበይባቸው እንጂ የፖለቲካ ማራመጃ ሜዳ መሆን እንደሌለባቸው፣ የትምህርት ሥራ ሙያ እንጂ ፖለቲካ አለመሆኑ፣ እንዲሁም በመልካም ተምሳሌትነት ሊጠቀሱ የሚገቡ የልሂቃን /Elite/ ት/ቤቶችና ዩኒቨርስቲዎች ሊፈጠሩ ይገባል። ትምህርት በዋናነት መፍትሄ ሰጪ ዕውቀት ካላስጨበጠና ችግር ፈቺ መሳሪያ ካልሆነ ለብዙሃኑ እንደሚታደል መሰረታዊ ሸቀጥ ካየነው አደጋው የከፋ የሀገር እድገት እንቅፋት ከመሆን የዘለለ ሚና እንደማይጫወት ይታወቃል፡፡ ስለዚህ የትምህርት ስርአታችን ከተደቀነበት ከፖለቲካ ተፅዕኖ ማላቀቅ ግድ ነው። ይህ ብቻ ሲሆን አምራችና በእውቀት የዳበረ ዜጋ ማፍራት ይቻላል። ትምህርት ቤቶች (ከፍተኛ የትምህርት ተቋማትን ጨምሮ) በግልፅም ሆነ በስውር የአንድ የፖለቲካ ፓርቲ ወይም ገዥ አካል ፖለቲካዊ አጀንዳ ማስፈፀሚያ መሆን የለባቸውም፡፡ ይህ ከሆነ ግን አሁን በሃገራችን እየተስተዋለ እንዳለው ውድቀቱ የከፋ ነው።

 

ኢትዮጵያችን በክብር ለዘላለም ትኑር!!!

 

ለአስተያየትዎ: kiduszethiopia@gmail.com ይጠቀሙ።

↧

እስራኤል ኢትዮጵያውያንን ጨምሮ 60ሺህ አፍሪካውያንን ከሃገሬ አስወጣለሁ አለች

$
0
0

ዛሬ በአዲስ አበባ ታትሞ የተሰራጨው አዲስ አድማስ ጋዜጣ እንዳስነበበው እስራኤል ኢትዮጵያውያንን ጨምሮ 60ሺህ የሚጠጉ አፍሪካውያን ስደተኞችን ከሃገሯ እንደምታስወጣ ያስታወቀች ሲሆን በህገወጥ መንገድ በሊቢያ የሚኖሩ ከ120 በላይ የሚሆኑ ኢትዮጵያውያን ደግሞ ወደ ሃገራቸው ይመለሳሉ ተብሏል፡፡ የእስራኤል ካቢኔ

(በአንድ ወቅት ቤተ እስራኤላውያን በ እስራኤል የሚፈጸመውን ዘረኝነት ተቃውመው ሰልፍ ሲወጡ የሚያሳይ ፎቶ ከፋይል)

(በአንድ ወቅት ቤተ እስራኤላውያን በ እስራኤል የሚፈጸመውን ዘረኝነት ተቃውመው ሰልፍ ሲወጡ የሚያሳይ ፎቶ ከፋይል)

ባለፈው እሁድ ስደተኞቹን የሚያስወጣ አዲስ ህግ ካፀደቀ በኋላ የሃገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤኒያዊን ኔትያሁ፣ ከ120 በላይ ኢትዮጵያውያን ከሊቢያ ይመለሳሉ  ህገወጥ ስደተኞቹን ከሀገራቸው እንደሚያስወጡ አስታውቀዋል፡፡ የአገሪቱ ካቢኔ ባፀደቀው መመሪያ መሰረት እስራኤል በመጀመሪያው ዙር 4ሺ ስደተኞችን የምታስወጣ ሲሆን በቀጣይም በዘላቂነት ህገወጥ ስደተኞች ወደ ሀገሯ እንዳይገቡ በዘላቂነት ለመከላከል ከግብጽ የምትዋሰንበትን ድንበር ጥበቃ እንደምታጠናክር ገልፃለች፡፡
ከሀገሪቱ ይወጣሉ ተበለው የሚጠበቁት አብዛኞቸ ሱዳናውያንና ኤርትራውያን ሲሆኑ ኢትዮጵውያኑም የገፈቱ ቀማሽ እንደሚሆኑ ተገልጿል፡፡ በሌላ በኩል ወደ አውሮፓ ለመሻገር ሊቢያን ማረፊያ ያደረጉ ከ120 በላይ ኢትዮጵያውያን በግብጽ ካይሮ ባለው የኢትዮጵያ ኤምባሲ ትብብር የጉዞ ሰነዳቸው ተዘጋጅቶላቸው በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር እና በአለማቀፍ የስደተኞች ተቋም (IOM) ትብብር እንደሚመለሱ ታውቋል፡፡
ይህ በእንዲህ እንዳለ በባህሬን በቤት ሠራተኝነት ተቀጥራ ትሠራ የነበረች ኢትዮጵያዊት በሶስት ወንዶች ተጠልፉ መደፈሯንና በሴተኛ አዳሪነት እንድትሰራ መገደዷን ገልፃ፤ ድርጊቱን ፈጽሟል የተባለውን ባንግላዲሻዊ እንደከሰሰች ሰሞኑን ተዘግቧል፡፡ የ28 አመቷ ኢትዮጵያዊት ቆሻሻ ለመድፋት ወደ ውጪ ስትወጣ ሁለት ማስክ ያጠለቁ ወንዶች አፍነው በመውሰድ አፓርታማ ቤት ውስጥ ከነበሩ አራት የተለያዩ አገራት ሴቶች ጋር በሴተኛ አዳሪነት እንድትሰራ መደረጓን ገልፃለች፡፡ በቀን አስር ጊዜ ያህል ከተለያዩ ወንዶች ጋር ወሲብ እንድትፈጽም ትገደድ እንደነበርም ለፍ/ቤት አስረድታለች፡፡

↧
Viewing all 15006 articles
Browse latest View live