Quantcast
Channel: Ethiopian News | ዘ-ሐበሻ | Latest News Provider | News For All
Viewing all 15006 articles
Browse latest View live

መድረክ በሳዑዲ መንግስት ላይ ስልፍ እንዳይወጣ በከለከለው ኢሕአዴግ ላይ ሰልፍ ሊወጣ ነው

$
0
0

- ሰላማዊ ሰልፉ ለህዳር 29 ተጠርቷል

በዘሪሁን ሙሉጌታ

የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ አንድነት መድረክ (መድረክ) በሳዑዲ አረቢያ በኢትዮጵያውያን ላይ የደረሰውን ጉዳት በመቃወም በሳዑዲ አረቢያ መንግስት ላይ የተቃውሞ ሰልፍ ቢጠራም መንግስት በአዲስ አበባ ከተማ ዓለም አቀፍ ስብሰባ ይካሄዳል፤ በቂ የፖሊስ ኃይል የለኝም የሚል ምላሽ መስጠቱን ተከትሎ መድረክ ተቃውሞውን በኢትዮጵያ መንግስት ላይ እንደሚያደርግ ገለፀ።
የአራት ፓርቲዎች ግንባር የሆነው መድረክ የተቃውሞ ሰልፉን በተመለከተ በመንግስት የተሰጠው ምላሽ የማያሳምንና የሕዝብን ብሦት በተዘዋዋሪ መንገድ የሚያፍን ተግባር በመሆኑ የሳዑዲ አረቢያ መንግስትን ለመቃወም ከሚደረገው ጥረት ጎን ለጎን የተቃውሞ ሰልፉ ሕዝብን እያፈነ ባለው መንግስት ላይ ማነጣጠሩን የወቅቱ የመድረክ ሊቀመንበር ዶ/ር መረራ ጉዲና በተለይ ለሰንደቅ ጋዜጣ ገልፀዋል።
merara gudina

ሰልፉ በመጪው ህዳር 29 ቀን 2006 ዓ.ም መነሻውን ስድስት ኪሎ የመድረክ ጽ/ቤት አድርጎ መድረሻውን የጠቅላይ ሚኒስትሩ ጽ/ቤት እንደሚሆን ዶ/ር መረራ ጨምረው ገልፀዋል።
“የኢትዮጵያ መንግስት የሳዑዲ አረቢያን መንግስት እንዳንቃወም አድርጎናል።” ያሉት ዶ/ር መረራ የኢትዮጵያ መንግስት በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ የሕዝቡን ብሦት በተቃውሞ እንዳይገልፅ አድርጓል። የኢትዮጵያ መንግስት ከሳዑዲ አረቢያ መንግስት ጋር ባለው ፍቅር ይሁን በሌላ ምክንያት ለጊዜው ግልፅ ባልሆነልን ምክንያት ተቃውሞአችንን በመከልከሉ የአሁን ሰላማዊ ሰልፍ በመንግስት ላይ ያተኮረ ነው ሲሉ ዶ/ር መረራ ተናግረዋል።
እስከአሁን ባለው ሂደት መንግስት ሕገ-መንግስታዊና ሰብአዊ መብት የሆነውን ተቃውሞን በሰልፍ የመግለፅ መሠረታዊ መብት አሳማኝ ባልሆነ መንገድ በመጣስ እየተረባረበ መሆኑን የጠቀሱት ዶ/ር መረራ ሕዝቡም ይህንኑ እንዲገነዘብልን ሲሉ ጠይቀዋል። “በአውሮፓና በአሜሪካ የሚገኙ መንግስታት ኢትዮጵያዊያን የሳዑዲ አረቢያ ኤምባሲዎች በሚገኙባቸው ከተሞች ሁሉ ሰላማዊ ሰልፍ እንዲያደርጉ እየፈቀዱ የሀገራችን መንግስት ግን ከራሱ አልፎ ሌሎችን ባዕዳን መንግስታትን እንዳንቃወም መከልከሉ አስገራሚም አሳዛኝም ነው” ሲሉ አያይዘው ገልፀዋል።
ባለፈው እሁድ ህዳር 6 ቀን 2006 ዓ.ም መድረክ ጠርቶት የነበረው ሰላማዊ ሰልፍ በከተማዋ በሚደረጉ ዓለም አቀፍ ስብሰባዎች እንዲሁም በቀጣይ የሚደረጉ ስብሰባዎች ስለሚኖሩ ሰላማዊ ሰልፍ ማካሄድ እንደማይቻል የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የሕዝባዊ ስብሰባና የሰላማዊ ሰልፍ ማሳወቂያ ክፍል ማስታወቁ አይዘነጋም። ባለፈው ቅዳሜ የክፍሉ ኃላፊ አቶ ማርቆስ ብዙነህ ይህንኑ የሚገልፅ ደብዳቤ ለመድረክ መላካቸው ታውቋል። በተመሳሳይ ሰማያዊ ፓርቲ ባለፈው አርብ በሳዑዲ አረቢያ ኤምባሲ አካባቢ የጠራው ሰልፍ እውቅና እንደሌለው በመንግስት በኩል ተገልጾ ለሰልፉ የወጡ ከሳዑዲ አረቢያ የመጡ ተሳታፊዎች ጭምር በፖሊስ መደብደባቸውና የፓርቲው አመራሮችና ጋዜጠኞች ጭምር ታስረው መፈታታቸው አይዘነጋም። (ምንጭ ሰንደቅ ጋዜጣ)

በዶ/ር መረራ ጉዲና መፅሐፍ ላይ
ሊደረግ የነበረው ውይይት ተሰረዘ

በዘሪሁን ሙሉጌታ

በቅርቡ ለሕትመት የበቃው “የኢትዮጵያ ፖለቲካ ምስቅልቅል ጉዞ እና የህይወቴ ትዝታዎች” በሚል ርዕስ ለሕትመት በበቃው መፅሐፍ ባለፈው አርብ ሕዳር 6 ቀን 2006 ዓ.ም በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ራስ መኮንን አዳራሽ ስድስት ኪሎ ካምፓስ ሊካሄድ የነበረው ውይይት ተሰዘረ።
ውይይቱ ተዘጋጅቶ የነበረው የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ እና የጀርመን ተቋም የሆነው የፍሬዲሪክ ኤቨርት ፋውንዴሽን ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካል ሳይንስ ዲፓርትመንት ጋር በመተባበር ነው። ተቋሙ ከዚህ በፊት የንባብ ባህልን በማበረታታት ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር በተለያዩ የሀገሪቱ ምሁራን በታተሙ መፅሐፎች ላይ ሕዝባዊና ምሁራዊ ውይይት ሲያካሂድ ቆይቷል። በህዳር 6 ቀን 2006 ዓ.ም ፕሮግራምም ላይ የመፅሐፉ ደራሲ ዶ/ር መረራን ጨምሮ ሌሎች ተጋባዥ ምሁራን አስተያየታቸውን የሚሰጡበት ፕሮግራም ተዘጋጅቶ በጉጉት ሲጠበቅ ነበር። በዩኒቨርሲቲው ቅጥር ግቢም የፕሮግራሙ ማስታወቂያ ተለጥፎ ሲያበቃ ለጊዜው ግልፅ ባልሆነ ምክንያት ለሌላ ጊዜ እንዲተላለፍ ተደርጎ የዕለቱ ዝግጅት ተሰርዟል።
የመፅሐፉ ደራሲ ዶ/ር መረራ ጉዳዩን በማስመልከት ለሰንደቅ ጋዜጣ እንደገለፁት፤ መፅሐፉ ኢህአዴግን ሳያስጨንቀው የቀረ አይመስለኝም ብለዋል። በተለይ ኢህአዴግ ኢትዮጵያን እየመራ ያለበት “ቀልድ” ሀገሪቱን የትም አያደርሳትም የሚለው የመፅሐፉ መደምደሚያ በኢህአዴግ ባለስልጣናት ላይ ቅሬታ መፍጠሩን አፍቃሪ መንግስት ከሆኑ የመገናኛ ብዙሃን ታትመው ከሚወጡ ፅሁፎች እየተረዳሁ ነው ብለዋል።
በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካል ሳይንስ ዲፓርትመንት ኃላፊ ዶ/ር ካሳሁን ብርሃኑ ስለጉዳዩ ጥያቄ ቀርቦላቸው የዩኒቨርሲቲው አስተዳደር አዳራሹን እንደሚፈልገው በመግለፁ ዝግጅቱ ለሌላ ጊዜ እንዲተላለፍ መደረጉን ለሰንደቅ ጋዜጣ አረጋግጠዋል። የፕሮግራሙ ዋና አዘጋጅ የጀርመን ተቋም የሆነው ፍሬድሪክ ኤቨርት ፋውንዴሽን መሆኑን ጠቅሰዋል። የዚህን ተቋም የፕሮግራም አስተባባሪ አቶ ያሬድ ፈቃደን አግኝተን ለማነጋገር ያደረግነው ጥረት ለጊዜው አልተሳካም።
“የኢትዮጵያ ፖለቲካና ምስቅልቅል ጉዞ እና የህይወቴ ትዝታዎች” የሚለው የዶ/ር መረራ መፅሐፍ በቅርቡ በሀገሪቱ ከወጡ የፖለቲካ መፅሐፎች አንዱ መሆኑ ይታወቃል።¾


የኃይሌ ገ/ሥላሴ ‘‘ታላቁ ሩጫ’’ ለሳዑዲ አረቢያ ጉዳት ለደረሰባቸው ወገኖች መታሰቢያ ሯጮች ሪቫን እንዳያደርጉ ከለከለ

$
0
0

በዘሪሁን ሙሉጌታ

Haile
በመጪው እሁድ በታላቅ ድምቀት በሚካሄደውና በአፍሪካ በግዙፍነቱ ቀዳሚ በሆነው ‘‘ታላቁ ሩጫ’’ ላይ የሚሮጡ ተሳታፊዎች በሳዑዲ አረቢያ ኢትዮጵያውያን ላይ የደረሰውን ጉዳት በሐዘን ለመግለፅ ጥቁር ሪቫን አድርገው እንዲሮጡ ሲል ሰማያዊ ፓርቲ ያቀረበውን ጥሪ የ‘‘ታላቁ ሩጫ’’ አስተባባሪዎች ተቃወሙ።
የፓርቲው ሥራ አስፈፃሚ አባላት በሳዑዲ አረቢያ የተፈናቀሉ ዜጎች ላይ የደረሰውን ግፍና በደል ለዓለም አቀፍ ህብረተሰብና ለኢትዮጵያ ሕዝብ ለማስገንዘብ በሩጫው የሚካፈሉ ተሳታፊዎች ጥቁር ሪቫን በማድረግ ሐዘናቸውን እንዲገልፁ ሲል ወስኗል። የታላቁ ሩጫ አስተባባሪዎች በጉዳዩ ላይ እንዲተባበሩና አጋርነታቸውን እንዲገልፁ ለማድረግ በደብዳቤ ጥያቄውም እንደሚያቀርብ የፓርቲው ህዝብ ግንኙነት አስታውቋል።
የታላቁ ሩጫ አስተባባሪዎች ግን የሰማያዊ ፓርቲ ጥሪ አንደግፈውም ሲሉ ጥሪውን ተቃውመዋል። ከአስተባባሪዎቹ አንዱ የሆኑት ዳግማዊት አማረ ለሰንደቅ ጋዜጣ እንደገለፁት ‘‘ፕሮግራሙ የስፖርት ዝግጅት ነው፤ ዓላማውም የተለየ ነው፤ ሕብረተሰቡን ማቀራረብና ሀገሪቱን በበጎ አይን ማስተዋወቅ ነው። ስፖርት ዋናው ተልዕኮው ሰላም ነው። በዝግጅቱም ላይ የራሳችን ዓላማ አለን። ሁሉም ሰው ለዚህ አላማ እንዲሮጥ ነው የምንፈልገው። ከዚህ ቀደም በተባበሩት መንግስታት የተቀየሱ ስምንቱ የልማት ግቦች እንዲሳኩ ባለፉት አራት አመታት ያንን ስናስተጋባ ቆይተናል። በዘንድሮ አመትም ‘‘ለተሻለች ኢትዮጵያ እንሩጥ’’ የሚል መልዕክት ነው ያለው’’ ብለዋል። በተጨማሪም ሁሉም የሩጫው ተሳታፊ በግዴታ የተሰጠውን ቲሸርት መልበስ አለበት። ሌላ ነገር የለበሰን ተሳታፊ እንደተሳታፊ አንቆጥረውም ሲሉ የገለፁት አስተባባሪዋ በቲሸርቱ ላይ የተፃፈው ‘‘ለተሻለች ኢትዮጵያ እንሩጥ’’ የሚለው መልዕክት እንዲስተጋባ እንፈልጋለን ሲሉ አስተባባሪዋ ጨምረው ገልፀዋል።
“ታላቁ ሩጫ” የራሱ አላማዎችን አንግቦ የሚካሄድ መሆኑን የጠቀሱት አስተባባሪዋ ዋነኛውና ቀዳሚው የኢትዮጵያን በጎ ገፅታ ማስተላለፍ፣ ተተኪ አትሌቶችን ማፍራት፣ እርዳታ ማሰባሰብና በጎ ገፅታን ማጎልበት ነው ብለዋል። ፕሮግራሙ በስፖርት ዝግጅትነቱ ይወሰድልን ሲሉም አሳስበዋል።
የሰማያዊ ፓርቲ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ ወጣት ብርሃኑ ተክለያሬድ ጉዳዩን በማስመልከት እንደገለፀው ፓርቲው ታላቁ ሩጫን ሐዘን ለመግለፅ ለመጠቀም የተገደደው ዜጎች እየሞቱ በመሆኑ ብሔራዊ የሐዘን ቀን መታወጅ ስላለበት ጭምር መሆኑን፤ መንግስት በዜጎች ላይ የደረሰውን ጉዳት በአግባቡ ገልፆ ብሔራዊ የሐዘን ቀን ማወጅ ሲገባው የቁጥር ጨዋታ ውስጥ በመግባቱ ነው ብሏል። ባለፈውም ቅዳሜ ብሔራዊ የእግር ኳስ ቡድኑም በተመሳሳይ ጥቁር ሪቫን አድርጎ እንዲጫወት ፓርቲው ማሳሰቡንም አያይዞ ገልጿል።
ታላቁ ሩጫ ስፖርታዊ መድረክ ሆኖ ሳለ ፖለቲካዊ ጉዳዩ ወደ ስፖርት ማምጣቱ ተገቢ አይደለም ለሚለው አስተያየት ወጣት ብርሃኑ ተጠይቆ ‘‘በሳዑዲ አረቢያ እየደረሰ ያለው የዜጐች ሰቆቃ የፖለቲካ ጉዳይ አይደለም። በሩጫው የሚሳተፉ ሰዎች ቁጥር ሪቫን ያድርጉ ስንል ሰማያዊ ፓርቲን ይደግፉ ማለታችን አይደለም። ለወገኖቻቸው ሰቆቃ ሐዘናቸውን ይግለፁ፤ ለአለም አቀፍ ህብረተሰብም ያስታውቁ ነው ያልነው’’ ሲል ከፖለቲካ ጋር የሚያያይዘው ነገር የለም ብሏል። ከዚህ በፊት ግራዚያኒን በመቃወማችን ፖለቲካ ተብሎ ነበር፤ አሁን ደግሞ የሳዑዲ መንግስት መቃወም የፖለቲካ ጉዳይ ብቻ ተደርጎ መወሰዱ ተገቢ አለመሆኑንም የህዝብ ግንኙነት ኃላፊው ጨምሮ አስታውቋል።
‘‘ታላቁ ሩጫ’’ በመጪው እሁድ ህዳር 15 ቀን 2006 ዓ.ም መነሻና መድረሻውን ጃንሜዳ በማድረግ ይካሄዳል። 500 ያህል የውጪ ሀገር ዜጎችን ጨምሮ 37ሺህ ተሳታፊዎች ይሳተፋሉ ተብሎ ይጠበቃል። ዜና ከሰንደቅ ጋዜጣ/ ርዕስ ከዘ-ሐበሻ

የፕሬዝደንት ኢሳያስ ከዕይታ መሰወር ምክንያት ምን ይሆን?

$
0
0

- መሰወራቸው አነጋጋሪ ሆኗል
- የአሜሪካ መንግስት ለዜጎቹ ማስጠንቀቂያ ሰጥቷል
- በአስመራ ጀኔራሎች መካከል የስልጣን ሽኩቻ ይጠበቃል

በሰንደቅ ጋዜጣ ሪፖርተር

በጥቅምት ወር 2006 ዓ.ም አጋማሽ በኤርትራ ጎዳና መታየታቸው የተነገረላቸው ፕሬዝደንት ኢሳያስ አፈወርቂ ከአደባባይ እና ከኤርትራ ቴሌቪዥን ዕይታ ውጪ መሆናቸው በአስመራ ከተማ ነዋሪዎች ከፍተኛ የሆነ መነጋገሪያ ርዕሰ ጉዳይ ሆኗል።
የሰንደቅ ጋዜጣ ዲፕሎማቲክ ምንጮች እንደገለፁት “ከዚህ በፊት ፕሬዝደንቱ ከሚሰቃዩበት የጉበት በሽታ ጋር በተያያዘ ለከፍተኛ ሕመም ተዳርገዋል። በአሁን ሰዓት በኳታር ሆስፒታል ሕክምና እየወሰዱ ይገኛሉ” ብለዋል።
isayas afewerki
በአስመራ ከተማ ውስጥ እየተናፈሰ ያለው ፕሬዝደንት ኢሳያስ አፈወርቂ ከበሽታቸው አገግመው ሀገር ሊያስተዳድሩ ይችላሉ የሚሉ በአንድ ወገን በሌላ ወገን ያሉት ከዚህ በኋላ ፕሬዝደንቱ ሀገር በሚያስተዳድሩበት ቁመና ውስጥ ሊገኙ አይችሉም የሚሉት ይገኙበታል።
ከዚህ ጋር በተያያዘ የአሜሪካ መንግስት እ.ኤ.አ. በግንቦት 10 ቀን 2013 ወደ ኤርትራ የሚጓዙ የአሜሪካ ዜጎች ከፍተኛ ጥንቃቄ እንዲያርጉ የሚያሳስብና ከተቻለ ወደ ኤርትራ ጉዞ እንዳያደርጉ የሚመክር የማሳሰቢያ መልዕክት በዚሁ ሳምንት በድጋሚ ለዜጎቹ አስተላልፏል።
“የኤርትራና የአሜሪካ ጥምር ዜግነት ያላቸው ዜጎች ካለምንም ቅድመ ሁኔታ ያስራቸዋል። ስለታሰሩ ዜጎች ከአሜሪካ መንግስት ማብራሪያ ሲጠየቅም ምላሽ አይሰጥም። አስመራ የሚገኘውም የአሜሪካ ኤምባሲ ዜጎቹ መታሰራቸውን ሰምቶ ማብራሪያ ለአስመራ መንግስት ቢያቀርብም ምላሽ አይሠጥም” ሲል መግለጫው ተቃውሞውን አሰምቷል።
በተለይ እ.ኤ.አ. ከ2012 ጀምሮ የኤርትራ መንግስት በግለሰብ ደረጃ ዜጎቹን አውቶማቲክ መሳሪያ በማስታጠቁ በቀላሉ የአሜሪካ ዜጎች ለአደጋ ተጋላጭ ይሆናሉ ከሚል ስጋት መሆኑን ለማወቅ ተችሏል። ታጣቂዎች በአስመራ ከተማ ሚሊሽያ በሚል ስለሚታወቁ ማንኛውንም ሰው በፈለጉት ቦታና ሰዓት መፈተሽ ይችላሉ። በዚህም የተነሳ በአስመራ የሚገኙ የቱሪስት መዳረሻና የሃይማኖት ቦታዎች ለመጎብኘት የሚመጡ የአሜሪካ ዜጎች በእነዚህ ታጣቂዎች ላይ ሊደርስባቸው ከሚችለው ስጋት ለመዳን ከአሜሪካ መንግስት ዕውቅና ውጪ እንዳይንቀሳቀሱ መግለጫው አሳስቧል።
በኦክቶበር 3 ቀን 2013 በላምባዱሳ ለተሰውት 350 ኤርትራዊያን ማስታወሻ በተደረገ ስነ-ስርዓት በኢትዮ-ኤርትራ ድንበር አካባቢ ኤርትራዊያን በመንግስታቸው ላይ ባሰሙት ቅሬታ ከፍተኛ ተቃውሞ መቀስቀሱ የሚታወቅ ነው።፡
የኢሳያስ አፈወርቂ ጤና መሻሻል ካላመጣ በአስመራ ወታደራዊ ባለስልጣናት መካከል የስልጣን ሹኩቻ መነሳቱ አይቀርም ሲሉ የዲፕሎማቲክ ምንጮቻችን ለሰንደቅ ጋዜጣ አስተያየታቸውን ገልፀዋል። አያይዘውም፤ ለምስራቅ አፍሪካ ሰላምም የራሱ የሆነ አሉታዊ ተፅዕኖ አለው ብለዋል።
የተባበሩት መንግስታት እ.ኤ.አ. 2009 የአስመራ መንግስት በሚከተለው የትርምስ የውጭ ግንኙነት ፖሊሲ መነሻነት በኤርትራ መንግስት ላይ ባስተላለፈው ማዕቀብ የተነሳ እስከ ዛሬ ድረስ የአስመራ መገናኛ ብዙሃን በአሜሪካ መንግስት ላይ ከፍተኛ የስም የማጥፋት ፕሮፖጋንዳ እየፈጸመ መሆኑ ይታወቃል።¾

ኢትዮጵያ፣ በህዳርና በ… ሁልጊዜ አስታውሳለሁ!! ከፕሮፌሰር አለማየሁ ገ/ማርያም

$
0
0

ከፕሮፌሰር አለማየሁ /ማርያም

ትርጉም በነጻነት ለሀገሬ

 

የህዳር ወር በኢትዮጵያውያን በአሰቃቂነቱ ሁልጊዜ ሲታወስ ይኖራል፡፡

november (1)

 

እ.ኤ.አ ኖቬምበር 2013 ሳውዲ አረቢያ ውስጥ በቃላት ለመግለጽ በሚዘገንን መልኩ በኢትዮጵያውያን/ት ላይ ሰቆቃ የተፈጸመበት ወር ነው፡፡ ላለፉት ጥቂት ዓመታት በሳውዲ አረቢያ በሚኖሩ፣ በሚሰሩና የፖለቲካ ጥገኝነት ለመጠየቅ ጥረት በማድረግ ላይ በሚገኙ ኢትዮጵያውያን/ት ላይ ስልታዊ የሆነ ጥቃት ሲሰነዘር ቆይቷል፡፡ እንዲያውም በግል በሚኖሩበት ቤት እምነታቸውን በማራመዳቸው ብቻ ኢትዮጵያውያኑ/ቱ ዜጎች ላይ የወንጀል ድርጊት ተፈጽሞባቸዋል፣ እንዲጋዙም ተደርጓል፡፡

እ.ኤ.አ 2011 የሰብአዊ መብት ተሟጋች ድርጅቱ (Human Rights Watch) ዘገባ የሳውዲ አረቢያ ፖሊስ “ህገወጥ ስብሰባ በሚል ሰበብ 35 የክርስትና እምነት ተከታይ ኢትዮጵያወያንን/ትን“ “በአንድ ኢትዮጵያዊ የክርስትና እምነት ተከታይ የግል መኖሪያ ቤት በእየሱስ ክርስቶስ የልደት በዓል ዋዜማ ተሰባስበው ጸሎት በማድረግ ላይ እንዳሉ” በፖሊስ ቀጥጥር ስር ውለዋል” ይላል፡፡ በአሁኑ ጊዜ በሳውዲ አረቢያ ጥገኝነት በሚፈልጉ እና ሌሎች ስደተኛ ኢትዮጵያውያት የቤት ሰራተኖች ላይ በሚደረገው ሰብአዊ መብት ረገጣ ምክንያት ምንጊዜም የማያቋርጥ ትችት እየተደረገ መሆኑን መግለጽ ማጋነን አይሆንም፡፡ በዚህ ወር በዕየለቱ በሚባል መልኩ የሳውዲ አረቢያ ፖሊሶች፣ የደህንነት ኃላፊዎችና ተራ የሳውዲ ዜጎች በየመንገዱ ኢትዮጵያውያን/ት ዜጎችን ያድናሉ፣ ይደበድባሉ፣ ያሰቃያሉ፣ አንዳንድ ጊዜም ይገድላሉ፡፡ የሳውዲ ፖሊሶች ኢትዮጵያውያንን ሲያሰቃዩ የሚያሳየው የቪዲዮ ቅርፅ ለህሊና የሚሰቀጥጥ ነው፡፡ የሳውዲዎች ኢትዮጵያውያንን በየመንገዱ የማባረር ሁከት፣ ጥቃት የመሰንዘርና የመግደል ድርጊት ምንም ዓይነት ማብራሪያ አያስፈልገውም፡፡ በአሁኑ ጊዜ ሳውዲ አረቢያ ውስጥ በኢትዮጵያውያን/ት ላይ የሚፈጸመውን የሰብአዊ መብት ረገጣ የሚያሳየው የፎቶግራፍ ምስል አስደንጋጭና ከሰለጠነ የሰው ልጅ አስተሳሰብ በእጅጉ የዘለለ ነው፡፡ በኢትዮጵያ ያለው ገዥ አስተዳደር 200 ሺ እና ከዚያ በላይ የሚሆኑትን በሳውዲ አረቢያ የሚኖሩትን ኢትዮጵያውያን/ት ለማገዝ ምን እያደረገ ነው? ምንም!!! እራሱ አምኖ በተቀበለው መሰረት ገዥው አስተዳደር ምን ያህል ኢትዮጵያውያን በሳውዲ አረቢያ እንደሚኖሩ እንኩዋን አያውቅም፣ ሆኖም ግን ተጨባጭነት በሌለው መልኩ ኢትዮጵያውያንን/ትን ከሳውዲ አረቢያ ሙሉ በሙሉ በተቻለ መጠን ወደ ኢትዮጵያ እመልሳለለሁ የሚል ቃል ገብቷል፡፡

የወባ ተመራማሪው “የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር”፣ ቴዎድሮስ አድሃኖም የሳውዲ መንግስት በግዛቱ በሚገኙት ስደተኛ ኢትዮጵያውያን/ት ሰራተኞች ላይ የፈጸመውን አረመኒያዊ የኃይል እርምጃ “መንግስቱ አውግዘዋል፡፡ ይኸ በፍጹም ተቀባይነት የለውም፡፡ ይህን ጉዳዩ የሳውዲ መንግስት እንዲያጣራ ጥሪ እናቀርባለን፡፡ እዚያ በነበሩበት ጊዜ በክብር መያዝ የነበረባቸውን ዜጎቻችንን ወደ ሀገራቸው ለመመለስም ደስተኞች ነን፡፡ ተቀባይነት የለውም” የሚለውን አባባል ገዥው አስተዳደር እንደ አስፈሪ የጭካኔ ድርጊቶች፣ ያለመሰልጠንነትና ዘግናኝ ጨካኝነትና ወንጀለኛነት የሚሉትን ቃላት ለመግለጽ የሚጠቀምበት የውግዘት ቃል ነው፡፡ አልጄዚራ እንደዘገበው ከሆነ በተፈጸመው ድርጊት ተበሳጭተው የነበሩ ኢትዮጵያውያን/ት አዲስ አበባ በሚገኘው የሳውዲ አረቢያ ኤምባሲ ፊት ለፊት በመገኘት ሰላማዊ ተቃውሟቸውን ለማሰማት በሄዱበት ጊዜ የገዥው አስተዳደር ፖሊስ በቁጥጥር በማዋል  ድብደባ ፍጽሞባቸዋል፡፡ “ፖሊሶች ከመጡ በኋላ ደብድበውናል፣ እና በአሁኑ ጊዜ ከ100 በላይ የሚሆኑ ሰዎች በእስር ቤት ይገኛሉ” በማለት የተቃዋሚው የሰማያዊ ፓርቲ ነባር አባል ጌትነት ባልቻ ገልጿል፡፡ ጌትነት በመቀጠልም “የፓርቲው ሊቀ መንበርና ምክትል ሊቀመንበር ከታሰሩት ውስጥ ይገኙበታል” በማለት ሀሳቡን አጠቃሏል፡፡

ሆኖም ግን ኢትዮጵያውያን/ በሀዳር ወር መጎዳትና መጎሳቀል ለምን ይደንቀን? እ.ኤ.አ በኖቬምበር 2005 ያለው የገዢ አስተዳደር ለመናገር በሚዘገንን መልኩ የጭካኔ ድርጊት በአትዮጵያኖች ላይ ፈፅሞአል:: በዚያው ዓመት የፓርላማውን ምርጫ ተከትሎ በግንቦት ወር በጠራራ ፀሐይ የተዘረፈውን የህዝብ ድምጽ በመቀወም ድምጻቸውን ባሰሙ ኢትዮጵያውያን/ት ዜጎች እራሱ መለስ ዜናዊ ያቋቋመው አጣሪ ኮሚሽን 193 ያልታጠቁ ወንዶች፣ ሴቶች እና ልጆች በአዲስ አበባ መንገዶች በሰላማዊ መንገድ ተቃውሟቸውን በመግለጻቸውና እና ሌሎች በከፍተኛ ደህንነት በእስር ቤት የሚገኙ እስረኞችን ሆን ተብሎ በጥይት ደብድበዋል፣ ሌሎች 763 የሚሆኑት በጽኑ ቆስለዋል፡፡

 

እ.ኤ.አ ከ2007 ጀምሮ በየጊዜው በህዳር ወር እ.ኤ.አ የ2005 ምርጫን ተከትሎ በመቶዎች የሚቆጠሩ ጨዋና ያልታጠቁ ሰልፈኞች ተኩስ በመክፈት ገደሏቸው፣ አካለ ጎደሎ አደረጓቸው፡፡ እኔም ያንን ጊዜ ለማስታወሰ ስል መጻፌን ቀጥየ ነበር፡፡

 

በመጀመሪያው የማሰታወስ ጽሁፌ እ.ኤ.አ በኖቬምበር 2005 እና በጁን 2005 የተከፈለው መስዕዋትነት ለዘላለም ይታወሳል! ለአንባቢ ዎቼም ሳስታዉስ በህይወት ላሉትና ለሞቱት ምስክርነት መስጠት እንዳለባችሁ የሞራል ግዴታ ተጥሎባችኋል ብዬ ነበር፡፡ ኤሊ ዌይሰል የዕልቂቱ ተራፊና የኖቬል ተሸላሚ በክብር እንዳስቀመጠው “ማስታዋስ አለብን ምክንያቱም የጋራ ትውስታችን የሆኑትን ያለፉ ድርጊቶች የወደፊቱን ትውልድ መብት መከልከል ስለማንችል ነው መርሳት መጥፎ ነገር ብቻ አይደለም ነገር ግን ስድብም ነው፡፡ የሞቱትን መርሳት ሁለተኛ ከመግደል እኩል ነው፡፡”

 

በ2005 ያለቁትን መርሳት ማለት በእነርሱ ላይ የተፈጸሙትን ግፎች መርሳት እንዲህም ያሉትን አረመኔአዊ ወንጀል መርሳትማለት ነው፡፡ እልቂቱን መርሳት ማለት ወንጀለኞች ተጠያቂ እንዳይሆኑ የልብ ልብ መስጠት ማለት ነው፣ ምክንያቱም ወንጀሎቹ ተረስተዋል፡፡ በመጨረሻም መርሳት ማለት በስልጣን ላይ ያሉ ወንጀለኞች እንደገና እና እንደገና የወንጀል ደረጃውን ከፍ በማድረግና ተጠያቂነት የሌለበትን ሁኔታ በመፍጠር ወንጀል እንዲሰሩ ማበረታታት ማለት ነው፡፡

አስታውሳለሁ! በምንም አይነት አልረሳምም፣ በፍጹም!!!

አስታውሳለሁ ምክንያቱም እኔ ካላስታወስኩ ማን ያስታዉሳል? አስታውሳለሁ ምክንያቱም የምረሳ ከሆነ ወንጀሎችና ወንጀለኞች ይረሳሉ፡፡ የምረሳ ከሆነ ታሪክ እንዴት ሊያስታውስ ይችላል? ታሪክ ሊያስታውስ የሚችለው ሌላ ሊያስታውስ የሚችል ሰው ሲኖር ነው:: በህዳር፣ በታህሳስ፣ በጥር፣ በየካቲት፣ መጋቢት፣ ሚያዝያ… ዛሬ ለኢትዮጵያ ወጣቶችና ነገ ለሚወለዱ ህጻናት አስታውሳለሁ፡፡

የእኔን ስራ በማድነቅና ለበርካታ ዓመታት ሲደግፉ ሲቆዩ ሌሎች ደግሞ ሲተቹ ሲቃወሙ የሚኖሩ አሉ። እኔ በኢትዮጵያውያን ሰበአዊ መብቶች ችኮ ነው ይሉኛል:: በኢትዮጵያውያን ሰበአዊ መብቶች ችኮ መሆን ለኔ ታላቅ ክበር ነው::

የ2005 ዕልቂትን አስታውሳሁ፡፡ እያንዳንዱን በግፍ የተገደሉትን አስታዉሳለሁ፡፡ አስታውሳለሁ ወጣት ሴቶች ወደፊት እናት ላይሆኑ፣ ወጣት ወንዶችን የአራዊቱን  ጭፍረኞች ገዳዮችን አልረሳም  ወደፊት አባት ላይሆኑ፣ ወላጅ የሌላቸውን ወላጆቻቸው የተገደሉባቸውን አስታውሳለሁ፡፡ ልጆቻቸው የተገደሉባቸውን እናቶችንና አባቶችን አስታውሳለሁ::

 

ወንጀለኞችን አልረሳም፣ ተንኮል የሰሩትን 237ቱን የፖሊስ አባላት አስታውሳለሁ፣ የወንጀለኞችን ቁንጮና መሪ የነበረዉን አራዊትን  አልረሳም:: የአራዊቱን  ጭፍረኞች ገዳዮችን አልረሳም::

 

አስታውሳሁ፣ መቼ ረሳለሁ: ሁልጊዜ  ህዳርን፣ ታህሳስን፣ ጥርን፣ የካቲትን፣ መጋቢትን፣ ሚያዝያን…. አልረሳም፡፡

.

ስም

ጾታ

እድሜ

ስራ

 

መግለጫ

1

ሬቡማ ኢርጋታ

34

ግንበኛ

2

መለሳቸው አለምነው

16

ተማሪ

3

ሀድራ ኦስማን

22

አይታወቅም

4

ጃፋር ኢብራሂመ

28

ቢዝነስ

5

መኮንን

17

አይታወቅም

6

ወልደሰማያት

17

7

ባህሩ ደምለው

አይታወቅም

8

ፈቀደ ነጋሽ

25

መካኒክ

9

አብርሀምይልማ

17

ታከሲ ነጂ

10

ያሬድ እሸቴ

23

ቢዝነስ

11

ከበደ ገ/ህይወት

17

ተማሪ

12

ማቴዎስ ፍልፍሉ

14

ተማሪ

13

ጌትንት ወዳጆ

48

ቢዝነስ

14

ቃሰም ራሽድ

21

መካኒክ

15

ሸውሞሊ

22

ቢዝነስ

16

አሊየ ኢሳ

20

የቀን ስራ

17

ሣምሶን ያዕቆብ

23

የህዝብ ማመላ

18

አለባለው አበበ

18

ተማሪ

19

በልዩ ዛ

18

ትራንስ. ረዳት

20

ዩሱፍ ጀማል

23

ተማሪ

21

አብርሃም አገኘሁ

23

ትራንስ.ረዳት

22

መሀመድ በቃ

45

አርሶ አደር

23

ረዴላ አወል

19

የታክሲ ረዳት

24

ሀብታሙ ኡርጋ

30

ቢዝነስ

25

ዳዊት ፀጋዬ

19

መካኒክ

26

ገዛኸኝ ገረመው

15

ተማሪ

27

ዮናስ አበራ

24

አይታወቅም

28

ግርማ ወልዴ

38

ሾፌር

29

ደስታ ብሩ

37

ቢዝነስ

30

ለገሰ ፈይሳ

60

ቢዝነስ

31

ተስፋዬ ቡሽራ

19

ጫማ ጠጋኝ

32

ቢንያም ደገፋ

18

ስራ አጥ

33

ሚሊዮን ሮቢ

32

ትራንስ.ረዳት

34

ደረጀ ደኔ

24

ተማሪ

35

ነብዩ ሃይሌ

16

ተማሪ

36

ምትኩ ምዋለንዳ

24

ዶመስቲክ ሰራተኛ

37

አንዋር ሱሩር

22

ቢዝነስ

38

ንጉሴ ዋብግነ

36

ዶመስቲክ ሰራተኛ

39

ዙልፋ ሀሰን

50

የቤት እመቤት

40

ዋስይሁን ከበደ

16

ተማሪ

41

ኤርሚያስ ከበደ

20

ተማሪ

42

00428

25

አይታወቅም

43

00429

26

አይታወቅም

44

00430

30

አይታወቅም

45

አዲሱ በላቸው

25

አይታወቅም

46

ደመቀ አበበ

አይታወቅም

47

00432

22

አይታወቅም

48

00450

20

አይታወቅም

49

13903

25

አይታወቅም

50

00435

30

አይታወቅም

51

13906

25

አይታወቅም

52

ተማም ሙክታር

25

53

በየነ በዛ

25

አይታወቅም

54

ወሰን አሰፋ

25

አይታወቅም

55

አበበ አንተነህ

30

አይታወቅም

56

ፈቃዱ ኃይሌ

25

አይታወቅም

57

ኤሊያስ ጎልቴ

አይታወቅም

58

ብርሃኑ ዋርካ

59

አሸብር መኩሪያ

አይታወቅም

60

ዳዊት ሰማ

አይታወቅም

61

መርሀጽድቅ ሲራክ

አይታወቅም

62

በለጠ ጋሻውጠና

አይታወቅም

63

ብኃይሉ ተስፋዬ

20

አይታወቅም

64

21760

18

አይታወቅም

65

21523

25

አይታወቅም

66

11657

24

አይታወቅም

67

21520

21

አይታወቅም

68

21781

60

አይታወቅም

69

ጌታቸው አዘዘ

45

አይታወቅም

70

21762

75

አይታወቅም

71

11662

45

አይታወቅም

72

21763

25

አይታወቅም

73

13087

30

አይታወቅም

74

21571

25

አይታወቅም

75

21761

21

አይታወቅም

76

21569

25

አይታወቅም

77

13088

30

አይታወቅም

78

እንዳልካቸው ገብርኤል

27

አይታወቅም

79

ኃይለማርያም አምባዬ

20

አይታወቅም

80

መብራቱ ዘውዱ

27

አይታወቅም

81

ስንታየሁ በየነ

14

አይታወቅም

82

ታምሩ ኃይለሚካኤል

አይታወቅም

83

አድማሱ አበበ

45

አይታወቅም

84

እቴነሽ ይማም

50

አይታወቅም

85

ወርቄ አበበ

19

አይታወቅም

86

ፈቃዱ ደግፌ

27

አይታወቅም

87

ሸምሱ ካሊድ

25

አይታወቅም

88

አብዱዋሂደ አህመዲን

30

አይታወቅም

89

ታከለ ደበሌ

20

አይታወቅም

90

ታደሰ ፌይሳ

38

አይታወቅም

91

ሶሎሞን ተስፋዬ

25

አይታወቅም

92

ቅጣው ወርቁ

25

አይታወቅም

93

ደስታ ነጋሽ

30

አይታወቅም

94

ይለፍ ነጋ

15

አይታወቅም

95

ዮሀንስ ኃይሌ

20

አይታወቅም

96

በኃይሉ ብርሀኑ

30

አይታወቅም

97

ሙሉ ሶሬሳ

50

አይታወቅም

98

የቤት እመቤት

አይታወቅም

99

ቴዎድሮስ

23

አይታወቅም

100

ጫማ ሰሪ

ጫማ ሰሪ

101

በኃይሉ ብርሃኔ

30

አይታወቅም

102

ሙሉ ሶሬሳ

50

የቤት እመቤት

103

ቴዎድሮስ ኃይሌ

23

ጫማ ሻጭ

104

ደጄኔ ይልማ

18

መጋዝን ጠባቂ

105

ኡጋሁን ወልደገብርኤል

18

ተማሪ

106

ደረጀ ማሞ

27

አናጺ

107

ረጋሳ ፈይሳ

55

ላውንድሪ ሰራተኛ

108

ቴዎድሮስ ገብረዎልድ

28

የግል ንግድ

109

መኮንን ገ/እግዚአብሄር

20

መካኒክ

110

ኤሊያስ ገ/ጊዮርጊስ

23

ተማሪ

110

አብርሀም መኮንን

21

የቀን ሰራተኛ

111

ጥሩወርቅ ገ/ጻድቅ

41

የቤት እመቤት

112

ሄኖክ መኮንን

28

አይታወቅም

113

ጌቱ ምሀትተ

24

አይታወቅም

114

ክብነሽ ታደሰ

52

አይታወቅም

115

መሳይ ስጦታው

29

የግል ንግድ

116

ሙሉአለም ወይሳ

15

አይታወቅም

117

አያልሰው ማሞ

23

አይታወቅም

118

ስንታየሁ መለሰ

24

የቀን ሰራተኛ

119

ጸዳለ ቢራ

50

የቤት እመቤት

120

አባይነህ ሰራሴድ

35

ልብስ ሰፊ

121

ፍቅረማርያም ተሊላ

18

ሾፌር

122

አለማየሁ ገርባ

26

አይታወቅም

124

ጆርጅ አበበ

36

የግል ትራንስፖርት

125

ሀብታሙ ዘገየ

16

ተማሪ

126

ምትኩ ገ/ስላሴ

24

ተማሪ

127

ትዕዛዙ መኩሪያ

24

የግል ንግድ

128

ፈቃዱ ዳልጌ

36

ልብስ ሰፊ

129

ሸዋጋ ወ/ጊዮርጊስ

38

የቀን ሰራተኛ

130

አለማየሁ ዘውዴ

32

የቴክስታይል ሰራተኛ

131

ዘላለም ገ/ጻድቅ

31

የታክሲ ሾፌር

132

መቆያ ታደሰ

19

ተማሪ

133

ሀይልየ ሁሴን

19

ተማሪ

134

ፍስሀ ገ/ጻድቅ

23

የፖሊስ ተቀጣሪ

135

ወጋየሁ አርጋው

26

ስራ ፈላጊ

136

መላኩ ከበደ

19

አይታወቅም

137

አባይነህ ኦራ

25

ልብስ ሰፊ

138

አበበች ሆለቱ

50

የቤት እመቤት

139

ደመቀ ጀንበሬ

30

አርሶ አደር

140

ክንዴ ወረሱ

22

ስራ ፈላጊ 141

141

እንዳለ ገ/መድህን

23

የግል ንግድ

142

አለማየሁ ወልዴ

24

መምህር

143

ብስራት ደምሴ

24

መኪና አስመጭ

144

መስፍን ጊዮርጊስ

23

የግል ንግድ

145

ወሎ ዳሪ

18

የግል ንግድ

146

በሀይሉ ገ/መድህን

20

የግል ንግድ

147

ሲራጂ ኑሩ ሰይድ

18

ተማሪ

148

እዮብ ገ/መድህን

25

ተማሪ

149

ዳንኤል ሙሉጌታ

25

የቀን ሰራተኛ

150

ቴዎድሮስ ደገፋ

25

የጫማ ፋብሪካ ሰራተኛ

151

ጋሻው ሙሉጌታ

24

ተማሪ

152

ከበደ ኦርቄ

22

ተማሪ

153

ለሊሳ ፋጤሳ

21

ተማሪ

154

ጃገማ ባሻ

20

ተማሪ

155

ደበላ ጉታ

15

ተማሪ

156

መላኩ ፈይሳ

16

ተማሪ

157

እልፍነሽ ተክሌ

45

አይታወቅም

158

ሀሰን ዱላ

64

አይታወቅም

159

ሁሴን ሀሰን ዱላ

25

አይታወቅም

160

ደጀኔ ደምሴ

15

አይታወቅም

161

ዘመድኩን አግደው

18

አይታወቅም

162

ጌታቸው ተረፈ

16

አይታወቅም

163

ደለለኝ አለሙ

20

አይታወቅም

164

ዩሱፍ ኡመር

20

አይታወቅም

165

መኩሪያ ተበጀ

22

አይታወቅም

166

ባድሜ ተሻማሁ

20

አይታወቅም

167

አምባው ጌታሁን

38

አይታወቅም

168

ተሾመ ኪዳኔ

65

የጤና ባለሙያ

169

ዮሴፍ ረጋሳ

አይታወቅም

170

አብዩ ንጉሴ

አይታወቅም

171

ታደለ በሀጋ

አይታወቅም

172

ኤፍሬም ሻፊ

አይታወቅም

173

አበበ ሀማ

አይታወቅም

174

ገብሬ ሞላ

አይታወቅም

175

ሰይዴ ኑረዲን

አይታወቅም

176

እንየው ጸጋዬ

32

እረዳት ትራንስፖርት

177

አብዱራህማን ፈረጅ

32

የእንጨት ስራ ባለሙያ

178

አምባው ብጡል

60

የቆዳ ፋብሪካ ሰራተኛ

179

አብዱልመናን ሁሴን

28

የግል ንግድ

180

ጅግሳ ሰጠኝ

18

ተማሪ

181

አሰፋ ነጋሳ

33

አናጺ

182

ከተማ ኡንኮ

23

ልብስ ሰፊ

183

ክብረት እልፍነህ

48

የጥበቃ ሰራተኛ

184

እዮብ ዘመድኩን

24

የግል ንግድ

185

ተስፋዬ መንገሻ

15

የግል ንግድ

186

ካፒቴን ደበሳ ቶሎሳ

58

የግል ንግድ

187

ትንሳኤ ዘገየ

14

ልብስ ሰፊ

188

ኪዳና ሹክሩ

25

የቀን ሰራተኛ

189

አንዷለም ሺበለው

16

ተማሪ

190

አዲሱ ተስፋሁን

19

የግል ንግድ

191

ካሳ በየነ

28

ልብስ ሽያጭ

192

ይታገሱ ሲሳይ

22

አይታወቅም

 

የጸጥታ ኃይሎች እርስ በእርስ ባደረጉት የተኩስ ልውውጥ በጥይት የተገደሉ ሰዎች፣

 

193

ነጋ ገብሬ

194

ጀበና ደሳለኝ

195

ሙሊታ ኢርኮ

196

የሃንስ ሶሎሞን

197 አሸናፊ ደሳለኝ

198

ፈይሳ ገ/መንፈስ

በመቶዎቹ የሚቆጠሩትን የግድያ ሰለባዎች፣ አካለ ጎደሎዎች፣ ቁስለኞች፣ በኃይል የተመቱትንና ሰውነታቸው በጥይት የተበሳሱትን ሁሉ አስታውሳለሁ፡፡

 

.. ኖቬምበር 2/2005 ከቃሊቲ እስር ቤት ለማምለጥ ሲሞክሩ በታጣቂዎች በተከፈተ ተኩስ በጥይት ተደብድበው ያለቁ ሰዎች ስም ዝርዝር፣

.

ስም

ጾታ

የተከሰሱበት ጥፋት፣

1

ጠይብ ሸምሱ መሀመድ

ለትጥቅ አመጽ በማነሳሳት

2

ሳሊ ከበደ

ምንም ዓይነት ክስ አልተጠቀሰም

3

ሰፊው እንድሪስ ታፈሰ

በአስገድዶ መድፈር

4

ዘገዬ ተንኮሉ በላይ

በዝርፊያ ወንጀል

5

ቢያድግልኝ ታመነ

የተወነጀሉበት ያልታወቀ

6

ገብሬ መስፍን ዳኘ

የተወነጀሉበት ምክንያት ያልታወቀ

7

በቀለ አብርሃም ታዬ

በህዝብ ላይ ሁከት በመፍጠር

8

ጉታ ሞላ

የተወነጀሉበት ምክንያት ያልታወቀ

9

ኩርፋ መልካ ተሊላ

በማስፈራራት ወንጀል

10

በጋሻው ተረፈ ጉደታ

የህዝብን ሰላም በማደፍረስ ወንጀል

12

አብደልወሃብ አህመዲን

በዘርፊያ ወንጀል

13

ተስፋዬ አብይ ሙሉጌታ

ለትጥቅ አመጽ በማነሳሳት

14

አዳነ ቢረዳ

በነፍስ ማጥፋት ወንጀል

15

ይርዳው ከርሴማ

የተወነጀሉበት ምክንያት ያልታወቀ

16

ባልቻ አለሙ ረጋሳ

በዝርፊያ ወንጀል

17

አቡሽ በለው ወዳጆ

የተወነጀሉበት ምክንያት ያልታወቀ

18

ዋለልኝ ታምሬ በላይ

በአስገድዶ መድፈር

19

ቸርነት ኃይሌ ቶላ

በዝርፊያ ወንጀል

20

ተማም ሸምሱ ጎሌ

የተወነጀሉበት ምክንያት ያልታወቀ

21

ገብየሁ በቀለ አለነ

የተወነጀሉበት ምክንያት ያልታወቀ

22

ዳንኤል ታዬ ለኩ

የተወነጀሉበት ምክንያት ያልታወቀ

23

መሀመድ ቱጂ ቀኔ

የተወነጀሉበት ምክንያት ያልታወቀ

24

አብዱ ነጂብ ኑር

የተወነጀሉበት ምክንያት ያልታወቀ

25

የማታው ሰርቤሎ

በአስገድዶ መድፈር

26

ፍቅሩ ናትናኤል ሰውነህ

በማስፈራራት ወንጀል

27

ሙኒር ከሊል አደም

በህዝብ ላይ ሁከት በመፍጠር

28

ኃይማኖት በድሉ ተሸመ

ጽንፈኝትን በማራመድ

29

ተስፋዬ ክብሮም ተኬ

በዥርፊያ ወንጀል

30

ወርቅነህ ተፈራ ሁንዴ

የተወነጀሉበት ምክንያት ያልታወቀ

31

ሲሳይ ምትኩ ሁነኛ

በማጭበርበር ወንጀል

32

ሙሉነህ አይናለም ማሞ

የተወነጀሉበት ምክንያት ያልታወቀ

33

ታደሰ ሩፌ የኔነህ

በማስፈራራት ወንጀል

34

አንተነህ በየቻ ቁበታ

ለትጥቅ አመጽ በማነሳሳት

35

ዘሪሁን መርሳ

በንብረት ላይ ጉዳት በማድረስ ወንወጀል

36

ወጋየሁ ዘሪሁን አስፋው

በዝርፊያ ወንጀል

37

በከልካይ ታምሩ

የተወነጀሉበት ምክንያት ያልታወቀ

38

የራስወርቅ አንተነህ

በማጭበርበር ወንጀል

39

ባዝዘው ብርሀኑ

ግብረሰዶም በመፈጸም ድርጊት

40

ሶሎሞን እዮብ ጉታ

በአስገድዶ መድፈር ወንጀል

41

አሳዩ ምትኩ አራጌ

በማስፈራራት ወንወጀል

42

ጋሜ ኃይሉ ዘገዬ

በህዝብ ላይ ሁከት በመፍጠር

43

ማሩ እናውጋው ድንበሬ

በአስገድዶ መድፈር ወንጀል

44

እጂጉ ምናለ

በግድያ ሙከራ ወንጀል

45

ኃይሉ ቦስኔ ሀቢብ

የተቀደሰን ቦታ በማራከስ

46

ጥላሁን መሰረት

የተወነጀሉበት ምክንያት ያልታወቀ

47

ንጉሴ በላይነህ

በዝርፊያ ወንጀል

48

አሸናፊ አበባው

የተወነጀሉበት ምክንያት ያልታወቀ

49

ፈለቀ ድንቄ

የተወነጀሉበት ምክንያት ያልታወቀ

50

ጀንበሬ ድንቅነህ ቢለው

በህዝብ ላይ ሁከት በመፍጠር

51

ቶሎሳ ወርቁ ደበበ

የዝርፊያ ወንጀል

52

መካሻ በላይነህ ታምሩ

የህዝብን ሰላም በማደፍረስ

53

ይፍሩ አደራው

የተወነጀሉበት ምክንያት ያልታወቀ

54

ፋንታሁን ዳኘ

የተወነጀሉበት ምክንያት ያልታወቀ

55

ጥበቤ ዋቀኔ ቱፋ

ለትጥቅ አመጽ በማነሳሳት

56

ሶሎሞን ገብረአምላክ

የህዝብን ሰላም በማደፍረስ

57

ባንጃው ቹቹ ካሳሁን

በዝርፊያ ወንጀል

58

ደመቀ አበጀ

በግድያ ሙከራ ወንጀል

59

እንዳለ እውነቴ መንግስቴ

የተወነጀሉበት ምክንያት ያልታወቀ

60

አለማየሁ ጋርባ

እ.ኤ.አ በ2004 ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ተማሪዎች አመጽ ጋር በተያያዘ መልኩ በቁጥጥር የዋሉ

61

ሞርቆታ ኢዶሳ

የተወነጀሉበት ምክንያት ያልታወቀ

 

ለምዘገባ፣ በዚህ እልቂት ላይ ተዋንያን የነበሩ 237 የተረጋገጠ የፖሊስ እና የደህንነት አባላት ዝርዝርን የያዘ ሰነድ ተቀምጧል፡፡

 

የኔሰው ገብሬን አስታውሳለሁ!

 

እ.ኤ.አ በ11/11/11 የኔሰው ገብሬ የተባለ የ29 ዓመት መምህር እና የሰብአዊ መብት ተሟጋች በደቡብ ኢትዮጵያ በዳውሮ ዞን በተርጫ ከተማ ከህዝብ መሰብሰቢያ ዳራሽ ፊት ለፊት እሳት በመለኮስ እራሱን በእሳት አያይዟል፡፡ ለሶስት ቀናት ቆስሎ ከቆየ በኋላ ህይወቱ ሊያልፍ ችሏል፡፡ እራሱን በእሳት ከማያያዙ በፊት የኔሰው ከህዝብ መሰብሰቢያ አዳራሽ ውጭ ለተሰበሰበ ህዝብ እንዲህ የሚል ንግግር አሰምቶ ነበር፣ “በእኩልነት ላይ ባልተመሰረተ አስተዳደር እና ፍትህ በሌለበት እንዲሁም የሰብአዊ መብት በማይከበርበት አገር ውስጥ እራሴን ለመስዋዕትነት አቀርባለሁ፣ ይህንንም በማድረጌ ወጣቱ ትውልድ ነጻ ይወጣል፡፡” የአትዮጵያ ጀግናዉ የእኔሰው ገብሬን አስታውሳለሁ

 

“ገዳዮችን አስታውሳለሁ፣ የግድያ ሰለባዎችንም አስታውሳለሁ፣ ለትግሌ የሚያግዙ አንድ ሺ እና ከዚያ በላይ ያሉ አሳማኝ ምክንያቶች እና ተስፋ ቢኖረኝም፡፡ ባስታወስኩ ቁጥር ተስፋየ ይሟጠጣል፣ ያንን ድርጊት ባስታውስኩ ቁጥር ደግሞ ተስፋቢስነቴን የማስወገድ ኃላፊነት እንዳለብኝ እገነዘበላሁ፣ ተስፋ ከተስፋቢስነት በላይ ነው፡፡“ ይላል ኤሊ ዊሴል!

 

**ለጥቃቱ ሰለባዎች ተጨማሪ መረጃ ይሆን ዘንድ የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብት ተሟጋች የሆኑት ያሬድ ኃ/ማርያም እ.ኤ.አ ሜይ 15/2006 በሰው ልጆች ላይ የተፈጸመ  ወንጀል በኢትዮጵያ፣ የጁንና ኖቬምበር 2005 የአዲስ አበባው ዕልቂት በሚል ርዕስ ለአውሮፓ ህብረት ፓርላሜንት ለልማትና ውጭ ጉዳዮች እና ለሰብአዊ መብቶች ንዑስ ኮሚቴ አስቸኳይ ጥምር ጉባኤ የቃረቡትን ምስክርነት ይመለከቷል፡፡

 

***የመርማሪ ኮሚሽኑ ሪፖርት ሙሉ በሙሉ የጥቃቱ ሰለባዎችን ነጻ ሲያወጣ አጠቃላይ ኃላፊነቱን ግን በፖሊስና ታጣቂ ኃይሎች ላይ ደፍድፎታል፡፡ መርማሪ ኮሚሽኑ አስተያየቱን በመቀጠል እንደሚከተለው አጠቃሎታል፣ “በተቃዋሚዎቹ የተጎዳ ንብረት የለም፣ በመንግስት በሞኖፖል በተያዘው መገናኛ ብዙሀን እንደተለፈፈው ጥቂት ተቃዋሚዎች የእጅ ቦንቦችንና ጠመንጃዎችን ታጥቀዋል እንደሚለው ሳይሆን በተቃራኒው የእጅ ቦንብ እና ጠብመንጃ የታጠቀ አንድም የተቀዋሚ አባል የለም፣ በመንግስት ታጣቂ ኃይሎች የተከፈተው ተኩስ ሰላማዊ ሰልፈኞችን ለመበተን ሳይሆን በተቃራኒው የሰልፈኞችን ጭንቅላትና ደረት ለመበርቀስ ዒላማ ያደረገ ነበር፡፡” የመርማሪ ኮሚሽኑ የ193 የእልቂቱ ሰለባዎችን ስም ዝርዝር የያዘ ሰነድ የሚያካትተው እ.ኤ.አ ከጁን 6 – 8 እና ከኖቬምበር 1- 4/2005 በዚህ ጊዜ ብቻ ያለውን ድርጊት እንዲያጣራ ለአጣሪ ኮሚሽኑ የተሰጠው ስልጣን ነበር፡፡ አጣሪ ኮሚሽኑ ግን በፓርላማው ከተሰጠው የጊዜ ገደብ ውጭ ከህግ ውጭ በመንግስት የፖሊስና የደህንነት ኃይሎች የተፈጸሙ ግድያዎችን ስም ዝዝዝር ያገኘ ቢሆንም እነዚህ ግድያዎች ኮሚሽኑ እንዲያጣራ ተለይቶ ከተሰጠው ጊዜ ውጭ በመሆናቸ ለህዝብ ይፋ ሳያደርገው ቀርቷል፡፡

 

 

 

 

በ1997ቱ የኢትዮጵያ ምርጫ ታዛቢ የነበሩት አና ጐሜዝ አዲስ አበባ ሊመጡ ነው

$
0
0

(ሪፖርተር)

Ana Gomez

አና ጐሜዝ

በ1997 ዓ.ም. በኢትዮጵያ በተካሄደው አገር አቀፍ ምርጫና ምርጫውን ተከትሎ ተከስቶ በነበረው የፖለቲካ ውዝግብ አካል የነበሩት የአውሮፓ ኅብረት የምርጫ ታዛቢ አና ጐሜዝ ወደ ኢትዮጵያ ሊመጡ ነው፡፡

በኢትዮጵያ በ1997 ዓ.ም. ተካሂዶ የነበረውን ምርጫ በአውሮፓ ኅብረት ተወክለው ምርጫውን በዋና ታዛቢነት የመሩትና የአውሮፓ ኅብረት ፓርላማ አባል የሆኑት አና ጐሜዝ፣ ምርጫውን አስመልክቶ ባወጡት ሪፖርት ኢሕአዴግ ከሚመራው መንግሥት ጋር ጥልቅ የሆነ ግጭት ውስጥ ገብተው ነበር፡፡

አና ጐሜዝ ከኢትዮጵያ መንግሥት ጋር በምርጫው ሳቢያ ውዝግብ ከገቡበት ጊዜ አንስቶ የኢሕአዴግን ፖለቲካ በተለይም የሰብዓዊ መብት አያያዙን ከመተቸት ተቆጥበው አያውቁም፡፡ ይሁን እንጂ ከምርጫው በኋላ ወደ ኢትዮጵያ መጥተው አያውቁም፡፡

በሚቀጥለው ሳምንት በኢትዮጵያ አስተናጋጅነት በሚካሄደው የአፍሪካ፣ የካረቢያንና የአውሮፓ ኅብረት አገሮች የጋራ የፓርላማ አባላት ጉባዔ ላይ ለመገኘት በአገሮቹ ከተወከሉ ግለሰቦች መካከል አና

ጐሜዝ እንዳሉበት በኢትዮጵያ በኩል 

የጉባዔው አስተባባሪ ከሆነው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ምንጮቻችን ለመረዳት ተችሏል፡፡ የኢትዮጵያ መንግሥት ለፖርቹጋላዊቷ የፓርላማ ተወካይ አና ጐሜዝ ቪዛ ሰጥቶ ይሁን ከልክሎ ለማወቅ ያደግነው ጥረት አልተሳካም፡፡ ይሁን እንጂ ግለሰቧ በቲዊተር ገጻቸው ላይ በአዲስ አበባው ጉባዔ ላይ እንደሚገኙ አረጋግጠዋል፡፡ አና ጐሜዝ በ1997 ዓ.ም. የኢትዮጵያ ምርጫ ትዝብት ሪፖርታቸው፣ ምርጫው ነፃና ፍትኃዊ እንዳልነበር ሪፖርት በማድረጋቸው ሪፖርቱ የውዝግቡ ምንጭ መሆኑ ይታወሳል፡፡ ይህንን ተከትሎ የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ሪፖርቱን ከማጣጣል አልፈው ግለሰቧን በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ላይ መዝለፋቸው ይታወሳል፡፡

አና ጐሜዝ በበኩላቸው እስከቅርብ ጊዜ ድረስ በኢትዮጵያ መንግሥት ላይ የዕርዳታ ማዕቀብ እንዲጣልበት እየሠሩ ይገኛሉ፡፡ ‹‹ዓለም አቀፉ ኅብረተሰብ በተለይም የእንግሊዝና የአሜሪካ መንግሥታት በኢትዮጵያ ዜጎች ላይ መንግሥት የሚፈጽመውን በደል እያዩ እንዳላዩ፤ እየሰሙ እንዳልሰሙ ችላ ብለዋል፤›› በማለት ከዓመት በፊት የሰላ ትችት በመሰንዘር የአውሮፓ ኅብረት ለኢትዮጵያ የሚደረገውን ዕርዳታ እንዲያቆም ተከራክረዋል፡፡

ዋሊያዎቹ የከበሩበት ምሽት

$
0
0

ዋሊያዎቹ(ሪፖርተር)  የይድነቃቸው ተሰማ ሌጋሲ እንዲቀጥል የኢሕአዴግ  ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር  ጥሪ አቀረበ

ከሁለት ዓመታት ወዲህ እመርታን ያሳየው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን (ዋሊያዎቹ) ከአገር አልፎ በአህጉር እንዲሁም በዓለሙ መድረክ ትኩረት የሳበው ከ31 ዓመታት ቆይታ በኋላ የአፍሪካን ዋንጫ መቀላቀሉ ብቻ አይደለም፡፡

በመጪው ሰኔ ብራዚል በምታዘጋጀው የዓለም ዋንጫ አፍሪካን ከሚወክሉት አምስት አገሮች አንዱ ለመሆን ከተፋለሙት 10 ምርጥ ቡድኖች አንዱ መሆኑ ጭምር ነው፡፡ በወሳኙ ምዕራፍ በደርሶ መልስ ውጤት በናይጄሪያ 4ለ1 (2ለ1 እና 2ለ0) ቢረታም፣ በአጨዋወቱ ብዙኀኑን ሲያስደምምና ቁጭ ብድግ ሲያደርግ ከርሟል፡፡ ተልዕኮውን ባለፈው ቅዳሜ በናይጄሪያዋ ካላባራ ከተማ በመጫወት ያጠናቀቀው ብሔራዊ ቡድን አዲስ አበባ በተመለሰ በማግስቱ ኅዳር 9 ቀን ምሽት በኢንተርኮንትኔንታል ሆቴል በተደረገ ልዩ ዝግጅት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ደመቀ መኰንንና ከፍተኛ ሹማምንት በተገኙበት የ2.7 ሚሊዮን ብር ሽልማት ለተጫዋቾቹና ለቡድኑ አባላት ተበርክቶለታል፡፡

በሥነ ሥርዓቱ ላይ ዋሊያዎቹን በማወደስ የተናገሩት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ደመቀ፣ በኢትዮጵያ በአፍሪካና በዓለም ስፖርትና ኦሊምፒክ መድረክ ሁነኛ ስፍራ የነበራቸው አቶ ይድነቃቸው ተሰማ የሄዱበትን ርቀት፣ ያሳለፉትን ሌጋሲ [ውርስ] ትውልዱ እንዲቀጥልበት ጥሪ አቅርበዋል፡፡ ከተጫዋቾቹና አሠልጣኞቹ ጋር ፎቶግራፍ የተነሱት ከቆሙት በስተግራ የስፖርት ምክትል ኮሚሽነር አምበሳ እንየው፣ የኢሕአዴግ  ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ደመቀ መኰንን፣ ከኋላ የፌዴሬሽኑ ፕሬዚዳንት አቶ ጁነዲን ባሻ፣ ከፊት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖም ከአሠልጣኝ ሰውነት ቢሻው ጋር ተጨባብጠው፤

የኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባር/ኢሕአግ/ ምልምል አርበኞችን አሰልጥኖ ማስመረቁን አስታወቀ

$
0
0

mreqa
ከአርበኞች ግንባር ለዘ-ሐበሻ የተላከ ዜና፡ የኢሕአግ የስልጠና ማዕከል ለወራት ያህል ለምልምል አርበኞች ሲሰጥ የነበረው ወታደራዊና ፖለቲካዊ ስልጠና በህዳር 12-2006 ዓ/ም አጠናቋል። ስልጠናውን የተካፈሉ ምልምል አርበኞች ከምልምል አርበኝነት ወደ ሙሉ አርበኛ መሸጋገራቸው ደስታ የፈጠረላቸው መሆኑን ገልጸው የድርጅቱ የስልጠና ማዕከል ያሰነቃቸው ወታደራዊና ፖለቲካዊ ስልጠና ቀድሞ ከነበራቸው የዕውቀትና የአካል ብቃት አንጻር የተሻለ አቅም የፈጠረላቸው መሆኑን ገልጸው የተማሩትን ትምህርት ወደ ተግባራዊ እንቅስቃሴ ለመቀየርና በአሁኑ ወቅት በሳውዲ አረቢያ በሚገኙ ወገኖቻችን ላይ እየደረሰ ያለውን ጥቃት ለማስቆም ሲንቀሳቀስ ባልታየው አምባገነኑ የወያኔ አገዛዝ ላይየአገርና የወገን ችግር ፈች ኢትዮጵያዊ ተልዕኮ ለመወጣት ራሳቸውን በቆራጥነት መንፈስ እንዳዘጋጁ አስታውቀዋል።
mreka
ተመራቂ አርበኞቹ አክለው እንዳብራሩት በተለይ በሳውዲ አረቢያ በሚገኙ ኢትዮጵያዊያንን ወገን እንደሌላቸው ሁሉ ታርደው በየጎዳናው መጣላቸው ሊታገሱት የማይችሉት አንገብጋቢ ጉዳይ እንደሆነ አስረግጠው ለዚሁ አጸፋ በእብሪተኛው ወያኔ ቡድን ላይ ጥቃት በመሰንዘር የወገን ደራሽ መሆናችንን እናስመሰክራለን ሲሉ በቁጣ መልክ ገልጸዋል። በህዳር 12-2006 ዓ/ም በተከናወነው የምልምል አርበኞች ምረቃ ስነ-ስርዓት የኢሕ አግ ከፍተኛ አመራር አባላት ተገኝተው እንኳን ለምረቃው ዕለት አደረሳችሁ ካሉ በኋላ በጽናት የኢትዮጵያን ተጠቅሶ የማያልቅ ተግዳሮት መፍትሂ ለመሻትና አንድነትና ዴሞክራሲ የሰፈነባት አገር ለመገንባት በሚደረገው ትግል የሚሰጣቸውን ግዳጅ ለመወጣት ከወዲሁ የስነ-ልቦና ዝግጅት እንዲያደርጉ ጠቁመዋል። በስልጠናው የተሻለ ብቃት ላሳዩ ተመራቂዎችና ሴት ተመራቂዎች ከአመራሩ የማበረታቻ ሽልማት ተቀብለዋል ዝግጅቱም በድርጅታዊ መዝሙር ጀምሮ ሞቅ ደመቅ ባለና የጀግኖችን ተጋድሎ በሚገልጽ መልኩ በድራማ፣ በስነ-ጽሁፍ፣ ቀስቃሽ በሆኑ ዘፈኖች፣ ቀረርቶዎች፣ በውታደራዊ ሰልፍ ትርኢትና በመሳሰሉት ትዕይንቶች ታጅቦ ተከብሯል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ የግንቦት 7 ሕዝባዊ ሃይልም በአቶ አንዳርጋቸው እና በአመራሩ ላይ የወያኔ ተላላኪ የግድያ ሙከራ ለማድረግ አቅዶ ሳይሳካለት ቀረ ባለበት ወቅት ወታደሮችን እንደሚያስመርቅ የገለጸ ቢሆንም ምርቃውን የሚያሳይ ፎቶ እስካሁን ለዘ-ሐበሻ የደረሳት ፎቶ የለም።

ኢትዮጵያ የአረብ ሠራተኛ አምራች ሃገር መሆኗ መቅረት አለበት

$
0
0

ከምኒልክ ሳልሳዊ

ኢትዮጵያውያን በመካከለኛው ምስራቅ በስፋት መሰደድ የጀመሩት ባለፈው 20 አመታት የወያኔው ጁንታ መንግስት ስልጣኑን ተቆጣጥሮ በህዝቦች ላይ በተለየ መልኩ የፈጠረውን አደገኛ የፖለቲካ እና የኢኮኖሚ ቀውስ ተከትሎ መሆኑ እሙን ነው::ይህ ቀውስ የደረሰባቸው ወገኖቻችን ከተሰደዱባት ሃገር አንዷ ሳኡዲ አረቢያ ተጠቃሽ ናት::ሳኡዲ አረቢያ ከሃብቷ ብዛት የመጣ የስራ ፍቅር ባሌለው ወጣት ዜጋ የተሞላች እና ፔትሮ ዶላር ባሰከራቸው ቱጃሮች የምትተዳደር አገር መሆኗ እና የዜጎቿ የስራ አለመስራት የስራ እድሎችን ስላሰፋ የወያኔ የፖለቲካ እና የኢኮኖሚ ተጠቂዎች ወደዚሁ መሰደድን መርጠዋል:: ይህንን ተከትሎም ይህን ሰሞን የአለም ዋና አጀንዳ የሆነው የኢትዮጵያውያን በሳኡዲ አረቢያ እየደረሰባቸው ያለ ስቃይ ነው::

maid2
ሰቆቃው ያደረሰው የሰብኣዊ መብት ጥያቄ ከሳኡዲ መንግስት ላይ ይልቅ ወደ ወያኔው ጁንታ ላይ እንዲተኮር ያደረገ ሲሆን የወያኔው ጁንታ ለከፍተኛ የፖለቲካ ኪሳራ ተዳርጓል::በኢትዮጵያውያን ላይ የደረሰው አስደንጋጭ እና ሰብኣዊነትን ያለፈ ድርጊት በመንግስት ባለስልጣናት መሃከል የፈጠረው መረበሽ እስከአለመግባባት አድርሷቸዋል::ይህንን የወያኔን አቋም የተመለከተችው ሳኡድ አረቢያ በአለም አቀፍ ደረጃ የፖለቲካ የበላይነት ተቀናጅታለች::የወያኔ ተቃዋሚ በሆኑት እና በአገር ውስጥ በውጪ በሚኖሩት ድርጅቶች እንዲሁን በከፍተኛ ደረጃ በአለም አቀፍ ደረጃ ባሉ ኢትዮጵያውያን እና እርትራውያን ዘንድ ከፍተኛ የሆነ አትኩሮት አግኝቶ የአለም ጎዳናዎች ሳኡዲን እና ወያኔን በሚቃወሙ በሰላማዊ ሰልፍ እየተጥለቀለቁ ነው::

ከወያኔው መንግስት የሚንጸባረቁ አጀንዳዎች ለዘብተኛ አቋሞች በስህተት እንደተፈጠሩ ወቅታዊ ሁኔታኦች እያሳዩ ሲሆን ስርኣቱ አጣብቂኝ ውስጥ እና የፖለቲካ ኪሳራ ውስጥ እንደገባ ተረጋግጧል:: የሌላ ሃገር እምባሲዎች ዜጎቻቸውን በመጠበቅ ላይ ሲያተኩሩ የወያኔው ዲፕሎማቶች የዜጎች ንብረት የሆነውን ኤምባሲ በመዝጋት አገልግሎት አቁመዋል::
የደረሰውን ሰቆቃ ተከትሎ ስርኣቱ ከፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር በመተባበር ለሉአላዊ የዜግነት ክብር መነሳሳት ሲኖርበት እና ህዝብን ማቀፍ ሲኖርበት ለብሄራዊ ውርደት ዜጎችን ዳርጓል::የፖለቲካ ፓርቲዎች የጠሩትን ሰልፍ በሃይል እና በደብዳቤ በትኗል::የወያኔው ስርኣት የህዝቡን ቁጣ ባለማንበቡ በችኮላ ያልበሰለ ሃሳብ በማራመዱ የፖለቲካ ኪሳራውን አስፍቶታል::ህገመንግስታዊ መብቶችን አለመከበሩን እና ለዜጎች አለመቆርቆርን በማሳየቱ በአለማቀፍ ደረጃ የኢትዮጵያውያንን ቁጣ ቀስቅሷል::ሚዲያዎች ከዜጎች የሳኡዲ ሰቆቃ ይልቅ የወያኔን ስርኣት ጋጥወጥነት አትኩሮት ሰተውታል::

(ፎቶ ፋይል ኢትዮጵያዊው በሪያድ ከተማ በፖሊስ ተይዞ)

(ፎቶ ፋይል ኢትዮጵያዊው በሪያድ ከተማ በፖሊስ ተይዞ)


ለዚህ ሁላ ችግር መንስኤው ስርኣቱ በልማት ሽፋን የሚከተለው የፖለቲካ እና እና የኢኮኖሚ ፖሊሲ ችግሮች እንደሆኑ አግጥጦ ገሃድ ከመውጣቱም በላይ የአደባባይ ሃቅ ሆኖ ለለውጥ እንትጋ የሚሉ ድምጾች በመላው ሃገሪቱ ተንጸባርቀዋል:; የወያኔ ስርኣት ህዝብን የሚያሳትፍ የፖለቲካ እና የኢኮኖሚ ፖሊሲ እስካልተከተለ ድረስ እና አሁን ባለው ሂደት ላይ ለውጥ እስካላደረገ ድረስ የስደት ችግሩ በስፋት እየቀጠል ይሄዳል:;ዛሬ ሳኡዲ ላይ የደረሰው ሰቆቃ ነገ በሌሎች ሃገራትም ይቀጥላል::ይህ ብሄራዊ ውርደት በታሪካችን አይተነው የማናውቅ ነው:;ኢትዮጵያውያን ከቀድሞው ጀምሮ በፖለቲካ ቢሰደዱም እንደዚህ አይነት ውርደትን አስተናግደው አያውቁም::የአሁኑ ውርደት ያለው ስርኣት ለዜጎቹ ደንታ ቢስ በመሆኑ የተወለደ ችግር ነው::በሃገሪቱ የኢኮኖሚ እድገት ተመዘገበ ከመባል ውጭ የተባለው እድገት ምንም አይነት ህዝባዊ ጠቀሜታ እንዳላሳየ በይፋ አስመስክሯል::የተማረው እና የሚሰራው ሃይል መሰደዱ ኢኮኖሚው እንደኮላሸ እንጂ እንዳደገ አያሳይም::የዚህ ሁላ መንስኤው ስርኣቱ የሚከተለው አፋኝ የፖለቲካ እና የእኮኖሚ ፖሊሲ ስለሆን ድጋሚ ሊከለስ እና ሊፈተሽ ይገባዋል::

የነቃ እና የተደራጀ አዲስ ፖሊሲ አስፈላጊ መሆኑ እሙን የሆነበት ጊዜ ላይ ደርሰናል::ስርኣቱ የሚከተለውን ፖሊሲ በአስቸኳይ ካልቀየረው የሚመጣው አደጋ ከፍተኛ ነው::በሃገሪቱ በልማት ስም እና በፖለቲካ ባላንጣነት በዜጎች ላይ የሚደርሰው ችግር የሙስና መንሰራፋት ሚዛናዊነት የጎደለው የምጣኔ ሃብት እንቅስቃሴ የግሉን ሴክተር የማዳከም ውስጣዊ ሴራ ዘር ተኮር የሆነ ፖለቲካ እና አድሎኣዊ አሰራር የትምህርት ጥራት መውረድ እና የስራ አጡ ቁጥር እንዲስፋፋ የሚደረጉ ደባዎች ዜጎች ምንም አይነት ጥያቄ እንዳያነሱ የሚደረጉ የፖለቲካ ዱላዎች ለድህነት መፈጠር እና የስደት መስፋፋት ምክንያት ሆነዋል::የህዝብ ቁጥርን ተከትሎ የሚደረግ የእድገት ፖሊሲ አለመመጣተን የሃገሪቱ ዜጎች ተዘዋውረው እንዳይሰሩ የተደረገ የጎሳ ፖለቲካ የተማሩ ዜጎችን የስራ እድል አጥብቦታል::አለ ተብሎ የሚወራለት የኢኮኖሚ እድገት ጥቂት የስርኣቱን ካድሬዎች ተጠቃሚ ያደረገ በመሆኑ ማንኛውም ነገር በካድሬዎች ዙሪያ እና በፓርቲ ስራዎች ዙሪያ ያተኮረ በመሆኑ ዜጎች በሃገራቸው ላይ ተስፋ እንዲቆርጡ አድርጓቸዋል::

ያለው ስርኣት ስርነቀል ለውጥ ለማምጣት ፖሊሲዎቹን እና የደረሱ የዜጎችን ችግር ከስሩ መሰረቱ መመርመር አለበት:: በፓርቲው አመራር ደረጃ ያሉ የስርኣቱ ባለስልጣናት ለስርነቀል ለውጥ ራሳቸውን ማዘጋጀት አለባቸው::በግል የንግድ ተቋማት ላይ ስርኣቱ ያለው አቋም ከመጀመሪያ ለውጦች አንዱ ነው የግል የንግድ ተቋማት መዳከም ምክንያቱ የስርኣቱ መራሽ የንግድ ድርጅቶች እና አድሏዊነት የፈጠረው የኢኮኖሚ ችግር ሲሆን መፍትሄውም የተዳከመውን የግሉን የንግድ እንቅስቃሴ እንዲያንሰራራ ማድረግ እና ለዜጎች በርካታ የስራ እድሎች እንዲከፍት ማበረታታን አንዱ ሲሆን የተለየ የፖለቲካ አቋም ያለው ዲያስፖራው በሃገሩ ጉዳይ እንዲሳተፍ እድሎችን ማመቻቸት እንዲሁ ለፖሊሲ ለውጥ ጅማሮ ሊሆን ስለሚችል ስደትን በስፋት ለመቀነስ እና ዜጎች ከሃገራቸው እንዳይወጡ ለማድረግ ይችላል::

በአሁን ሰአት ስርኣቱ እየተተቀመበት ያለው የኢኮኖሚ ፖሊሲ በተጭበረበረ ፖለቲካ ላይ የተገነባ ከመሆኑም ባሻገር ባልተማሩ እና ባልሰለጠኑ የፖለቲካ ታማኞች ስለሚተገበር በአግባቡ እየተተረጎመ ባለመሆኑ ውድቀትን አምጥቷል::የሃገሪቱ አጠቃላይ ሃብት እና የኢኮኖሚ ምሶሶ በጥቂት የፓርቲ ድርጅቶች እና ባለስልጣናት እጅ በቁጥጥር ስር ስለሆነ የግሉ ኢንቨስትመት በመዳከሙ እና ስርኣቱ ከዚህ አይነት የንግድ እንቅስቃሴ ካልወጣ በቀር ምንም አይነት ለውጥ መምጣት እንደማይቻል እሙን ሲሆን መፍትሄው የተቆጣጠረውን እና በግል መያዝ ያለባቸውን የንግድት ተቋማት እና የአገልግሎት ዘርፎች መልቀቅ ካልቻለ ችግሩ እየከፋ ዜጎችን ምንም ተጠቃሚ እንዳይሆኑ ያደርጋል::በአለም አቀፍ ደረጃ እንደሚታየው መንግስታት ህግ የማውጣት እና የማስፈጸም አቅም እንጂ ከትልቅ እንስከተራ ንግድ ድረስ እጃቸውን አስገብተው ሲሰሩ አይታይም::ያለው ስርኣት ወደ ቸርቻሪ ነጋዴነት በመቀየሩ ለዜጎች የስራ እድሉን አጥብቦታል::

ኢኮኖሚውን ከፍተኛ የጦር ጄኔራሎች እና የፓርቲ የንግድ ድርጅቶች በሞኖፖል ስለተቆጣጠሩት ዜጎች በስርኣቱ ፖለቲካ ካልተጠመቁ ድረስ ስራ የማግኘት እድል የላቸውም::ይህ ኢኮኖሚውን የመቆጣጠር የፖለቲካ ጭብርብሮሽ የኢንቨስትመት ሂደቱን ከማዳከሙም በላይ ዜጎች በሃገራቸው እና በስርኣቱ ላይ እምነት እንዲያጡ አድርጓል::ስርኣቱ ከነጋዴነት መውጣት ሰፊ የስራ እድሎች እንዲፈጠሩ እና ስደት እንዲቀንስ የሚረዳ ሲሆን ዜጎች በሃገራቸው ተሳፋ እንዳይቆርጡ ያደርጋል:: እንዲሁም የመንግስት የመገናኛ ቡዙሃን በሃሰት የተሞሉ መሆናቸው እና አስፈላጊውን መረጃ መስጠት አለመቻላቸው ሌላኛው የኢኮኖሚ ድቀት እና የስደት መንስኤ ናቸው:: በነጻነት የማይሰሩት እና ለፖለቲካው የእድሜ ማስረዘሚያ የሆኑት የመገናኛ ብዙሃን ቀረጥ የሚከፍላቸውን ህዝን እንዳያገለግሉ ከመደረጉም በላይ በሃሰት የፖለቲካ እና የኢኮኖሚ ወንጀሎችን በመፈብረክ የታወቁ ሆነዋል::

ሕዝቡ ስርኣቱ እስካልተመቸው ድረስ ስደትን ማቆም አይቻልም ጊዜአዊ እገዳውም ውጤታማ አይሆንም:: ሀገሪቱ ብዙ ሴቶች ወደ መካከለኛው ምስራቅ ሊሰደዱባት የቻለውም ከሴቶች እኩልነት ጋር በተያያዘም ችግር በመኖሩና ብዙ ስራ አለመሰራቱን የሚያሳይ ነው::በዚህ ዙሪያ የሚሰሩ ድርጅቶችም በነፃነት አለመቋቕውማቸው ሴቶችም እንደሰው አለመታየታቸው ነው::የፓርቲ ፖለቲካ መስበክ ሳይሆን በሴቶች እኩልነት እና ተሳትፎ ዙሪአ ኢኮኖሚው መዳበር ሲኖርበት አስፈላጊውን ኦረንቴሽንም መስጠን የስርኣቱ ግዴታ ነው::አሁን ባለው ሁኔታ ወደ ስራ የሚገባውን ወጣት የሚሸከም ኢኮኖሚ አልተፈጠረ:: የግል ሴክተሩም በርካታ ዜጎች እንዳይፈጥር ሆኖ እየሞተ መሆኑን ከዓለም ባንክ ሪፖርቶች ማየት ይቻላል::በዓለም ደረጃ በመንግስት ኢንቨስትመንት ኢትዮጵያ በዓለም ሦስተኛ ስትሆን፤ በግል ኢንቨስትመንት ከመጨረሻዎቹ ስድስተኛ ደረጃ ላይ ነን። ስለዚህ የግል ሴክተሩ ካልተስፋፋና ካላደገ ስራ ሊፈጠር አይችልም። በየዓመቱ ከዩኒቨርሲቲ የሚመረቀው ወጣት በዓመት ወደ መቶ ሺህ ሊጠጋ ነው። ይሄንን ኃይል መጦ የሚያስቀር የሚያደርግ ኢኮኖሚ መፈጠር የሚቻለው የግል ሴክተሩ ሲነቃቃ ነው። አሁን የግል ሴክተሩ በኮንስትሪክሽን ዘርፍ ላይ ውር ውር እያለ ነው። ይሄም ሴክተር ቢሆን፤ የቀን ሰራተኛ ከመሳብ ባለፈ ሙያተኛውን መቅጠር አልቻለም። ለዚያውም ትንሽ ሲሚንቶ መለሰን ሲጀምሩ ወደ መካከለኛው መስራቅ በተከበረ ወርሃዊ ደመወዝ ሲቀጠሩ ይታያል። ሀገሪቱ የተማረ የሰው ኃይል የላትም። ያሉዋትም ለባዕድ አገር እያገለገሉ ነው። በአንፃሩ የአገሪቱን የባቡር መንገድ እና ግድብ የሚሰሩት ቻይናና ሕንድ ናቸው። ስኳር ፋብሪካውንም የሚሰሩት ሕንዶች ናቸው። በሚያሳዝን መልኩ ሁለት ሚሊዮን የሚሆኑ ኢትዮጵያዊያን የተማሩም ሆነ ያልተማሩ ችሎታቸውን እየሸጡ ያሉት ለባዕድ ሀገር ነው። ከአፍሪካ እስከ ደቡብ ሱዳን፣ ቦትስዋና እና ደቡብ አፍሪካ ሳይቀር በርካታ ኢትዮጵያውያን ችሎታቸውን በጥሩ ዋጋ እየሸጡ ነው። ይሄን አሳዛኝ ታሪክ ለመቀየር የግል ሴክተሩ ማደግ ወሳኝ ነው ።

የግል ዘርፉ የሀገሪቱን ኢኮኖሚ ይረከብ ማለት ግድብ ይገንባ፣ የባቡር መንገድ ይዘርጋ ማለት አይደለም ነገር ግን የግል ዘርፉ ሊሰራቸው የሚችሉ ስራዎች ተለይተውና ተጠንተው መሰራት አለባቸው። የኅብረተሰብ ችግርም እየተበራከተ ስለሆነ ችግሩን መመርመር ያስፈልጋል ። የግል ዘርፉ ከካፌና ሆቴል ላይ ብቻ የሚሯሯጠው ለምንድነው? የቀጥታ የውጪ ኢንቨስትመንት ችግር በገፍ የማይመጣው ለምንድነው፣ አነስተኛና ጥቃቅን አደረጃጀት ምን ያህል ውጤት አምጥቷል? የተደራጀ ጠንካራ የግል ዘርፍ መፍጠር ነው ወይስ አነስተኛ ጥቃቅን ድርጅቶች የሚለው መታየት አለበት። የትኛው ነው ብዙ ኀሳብ የሚያመነጩት፣ የገበያ ሁኔታስ? ባንኮች አካባቢ ያለው ችግር ምንድነው? ለምን አያበድሩም ይሄ ሁሉ መፈተሽ አለበት ።ኢትዮጵያ የአረብ ሠራተኛ አምራች ሃገር መሆኗ መቅረት አለበት ።


አሁንም የድረሱልን ጥሪ ከሳዑዲ አረቢያ እስር ቤት (Video)

$
0
0

(ዘ-ሐበሻ) ከሳዑዲ አረቢያ ወደ ኢትዮጵያ መንግስት እስካሁን በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎችን እንዳጓጓዘ ቢገልጽም አሁንም በሳዑዲ ያሉ እህቶች በቪድዮ የተደገፈ ስቃያቸውን ለዓለም እያሰሙ ነው። የኢትዮጵያ ህዝብ ይድረስልን እያሉ የሚናገሩት እነዚሁ እህቶች ለ2 እና ለ3 ወራት እስር ቤት እንደቆዩም ይናገራሉ። አንዳንድ የደረሱን መረጃዎች ደግሞ የኢትዮጵያ መንግስት ቅድሚያ ሰጥቶ ወደ ሃገር እያሳፈረ ያለው የስርዓቱ ደጋፊ የሆኑ፣ ኢምባሲው በሚጠራቸው ስብሰባዎች የሚገኙ፣ ገንዘብ በሙስና ለሚከፍሉ ነው የሚሉና ሌሎችም ናቸው። አንድ ዜጋ የመንግስትን አገልግሎት ለማግኘት የግድ የመንግስት ስብሰባዎች ላይ መገኘትና የነርሱን ፖለቲካ አቀንቃኝ መሆን የለበትም፤ መንግስትን መደገፍም መቃወምም የሰው ልጅ መብት ሲሆን መንግስት ደግሞ የሚጠላውንም የሚወደውንም የማገልገል ሃላፊነት አለበት። ሕሊና ያለው መንግስት የሚያስበው ይህን ነው። የእህቶቻችንን ጥሪ ይመልከቱ፦

አሁንም የድረሱልን ጥሪ ከሳዑዲ አረቢያ እስር ቤት (Video)

ለሕዝቡ ግደ የለሹ የኢህአዲግ መንግስት መወገድ አለበት

$
0
0

November 21/2013

ገዛኸኝ አበበ ከኖርዌይ

 ሰሞኑንን በሳዑዲ አረቢያ በኢትዮጵያውያን እየደረሰ ያለው ግፍና በደል የብዙዎቻችን ኢትዮጵያኖች አይምሮ የጓዳ እና ያሳዘነ ነገር ነው እርግጠኛ ነኝ ማንም ኢትዮጵያዊ ዜጋ በወገኖቻችን ላይ እየደረሰ ያለውን  መከራ በቸልተኝነት እንደማይመለከተው ምክንያቱም እየሆነ ያለው ነገር ኢትዮጵያዊ ክብርን የሚነካ እና አንገትን የሚያስደፋ ነገር ነው :: ወንድሞቻችን ተገርፈዋል ተደብድበዋል እንደ እንስሳ በአደባባይ ተቀጥቅጠዋል  የኢትዮጵያዊነትን ክብር የሆነውን ባንዲራ እንደያዙ በአደባባይ ተገለዋል ሴት እሕቶቻችንም ሳይቀሩ እንደዚሁ ዘግናኝ እና አሳፋሪ የሆነ በደል እየደረሰባቸው ነው:: እህቶቻችን በጨካኝ እና በአረመኔ የሳውዲ ጎረምሶች እና ፖሊሶች ተደብድበዋል ክብራቸው ተዋርዶል ተደፍረዋል ይህ ሁሉ በወገኖቻችን እየደረሰው ያለው ነገር ወደ ህዝብ ጆሮ ከደረሰበት ጊዚ ጀምሮ የመላው ኢትዮጵያንን ቁጣ በሀይል እና በንዴት የቀሰቀሰ ሲሆን ከየስፍራው እነዚህ ወገኖቻችን ላይ እየደረሰ ያለው ሰይጣናዊ እና አረመናዊ ድርጊት እንዲቆም የኢትዮጵያኖ ጩኽት ከዳር እስከ ዳር በየሀገሩ እንደቀጠለ ይገኛል::ማንም ኢትዮጵያዊ የትኛውም ብሔር ቤሆን በወገኖቻችን ላይ የደረሰው በደል ያላሳዘነው ያላስቆጨው እና በህልኽ ያልቀሰቀሰው ያለ አይመስለኝም ኢትዮጵያን እና የኢትዮጵያን ዜጓች እንደ ወንድም እና እህቶቻቸው የሚያዩ ኤርትራውያን ወገኖቻችን ሳይቀሩ ይህን በወገኖቻችን ላይ እየደረሰ ያለውን ግፍ እና በደል በአደባባይ በመውጣት እያወገዙ ይገኛሉ::
ዜጕች ሀገራቸውን ጥለው ከሀገር እየወጡ ለስደት እና ለመከራ የሚዳረጉበት ምክንያት ብልሹ የሆነው የወያኔ የኢህአዲግ መንግስት አስተዳደር እንደሆነ በሁሉም ዘንድ የታመነበት ሀቅ ነው:: በሳውዲም ለወንዶች እና ለሴቶች እህቶቻን መሰቃየት፣ መሞት እና ማለቅ  ቁጥር አንድ ተጠያቄው ይሄው አገሪቷን እየመራው ነው ብሎ የሚናገረው ለሃያ ሁለት አመታት በስልጣን ወንበር ላይ ቁጭ ብሎ ለኢትዮጵያ ህዝብ አንዳችም ሊፈይድ ያልቻለው በምትኩ ግን ህዝብን ለስደት  እና ለሞት የዳረገው ይኼው የወያኔ መንግስት እንደሆነ በብዙዎች ዘንድ እየተነገረ ይገኛል:: በርግጥም ሰሞኑን በኢትዮጵያውያን ላይ እየደረሰ ያለው መከራ ለመላው ኢትዮጵያውያን ሕዝቦች የኢህአዲግን መንግስት እንኮን ሳይቀር እየደገፉ ላሉ ወገኖቻችን የወያኔ ኢህአዲግ መንግስት ምን ያክል የኢትዮጵያን ሕዝብ ጥቅም ለማሰከበር ያልቆመ እና  ለሚመራው እና ተወክዪለታለው ለሚለው ሕዝብ ግድ የሌለው እንደሆነ በተግባር በአደባባይ እያሰመሰከረ ይገኛል ::

በሳውዲ የሚገኙ ዜጐቻችን   የወገን እና የሀገርን እርዳታን በሚሹበት በአሁኑ ሰአት የወገን እና የሀገር ህልውና እየተረገጠበት ባለበት ሰአት የኢህአዲግ መንግሰት ግን ጆሮ ዳባ ልበስ በማለት ለህዝባቸን ምንም ያክል እርዳታን አለማድረጉ በብዙዎች ዘንድ በርግጥ ኢትዮጵያ ውስጥ መንግስት አለ ወይ እያስባለ ነው የሚገኛው ::   ይህም ብቻ አይደለም በሳውዲ እየተፈፀመ ያለውን በደል በመቃወም በዓለም አቀፍ ደረጃ ኢትዮጵያዊያን ድምፃቸውን በማሰማት ላይ በሚገኙበት በአሁኑ ሰአት ሰአት በሀገር ቤት የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን ግን በገዛ ሀገራቸው በዜጐቻችን ላይ እየደረሰ ያለውን በደል ለመቃወም አልታደሉም :: በርግጥም እራሱን ትዝብት ላይ የሚጥለውን ተግባር በመፈጸም ድምጻቸውን ለማሰማት የወጡትን ዜጐች በመደብደብ በመግረፍ እና በማሰር ከሳውዲ አረቢያ መንግሥት ጐን በመቆም ዋና ተባባሪ መሆኑን  አስመስክሯል  አልፏል:: ይህ ሁሉ ሲሆን በራሱ በወያኔ ደገፊዎች ሳይቀር የወያኔ መንግስት እየተወገዘ እና እየተብጠለጠለ ይገኛል ምክንያቱም ነገሩ የፖለቲካ ነገር ጥያቄውም የፖለቲካ ጥያቄ እንዳልሆነ መላው የኢትዮጵያ ህዝብ በሚገባ ጠነቅቆ ያውቀዋል እና:: በሳውድ አረቢያ በወገኖቻችን ላይ እየደረሰ ያለው በደል በጣም ያላስቋጨው እና ያላንገበገበው ኢትዮጵያዊ የለም አንድ የወያኔ የኢህአዲግ መንግስት እንደሆነች በሚገባ የማውቃት ከሀገር ውጭ የምትኖሩር በዜጓቻችን ላይ እየደረሰ ያለው ግፍ የሳዘናት እና የመንግስት ግድ የለሽነት ያናደዳት ወጣት አትንኩብኝ እያለች በፊስ ቡክገጽ ሳይቀር ስትክበው የነበረችውን መንግስት በመቃውም በፊስ ቡከ ገጾ ላይ እንዲህ አለች የኢትዮጵያ መንግስት ሆድ እንጅ ጭንቅላት የለውም :: እውነቷን ነው ይህች ወጣት እህታችን  ለሆድ ሳይሆን በሚገባ ህዝቡን ለመመራት እና ለማስተዳደር የተቀመጠ መንግስት ቢሆን ኖሮ በሳውዲ በዜጐቻችን ላይ እየደረሰ ያለው ስቃይ ግድ ብሎት የወገን አጋርነቱን ያሳይ ነበር ይህንን ግን የወያኔ መንግስት ሊያደርገው አልቻለም::ስለዚህም ለዜጕቹ ግድ የሌለው መንግስት ለህዝብ ጥቅም የቍመ መንግስት ስለሆነ መወገድ አለበት ::አምላክ በስቃይ ውስጥ ያሉትን ወገኖች ይጠብቃቸው

ከአዲስ አበባ ከአቡነ ማቲያስ ጋር የመጣው የፓትርያርኩ ልዩ ካሜራ ማን (ዲያቆን) አሜሪካ ላይ ጠፋ

$
0
0

በፓትሪያርክነት ከተሾሙ በኋላ ለመጀምሪያ ጊዜ ወደ አሜሪካ የመጡት አቡነ ማቲያስ አብረዋቸው ከኢትዮጵያ ከመጡ አገልጋዮቻቸው መካከል አንዱ የሆነው ዲያቆን አሁን ደረሰ እዚሁ አሜሪካ ጠፍቶ መቅረቱን የዘ-ሐበሻ ታማኝ ምንጮች ገለጹ።
liyu camera man
የፓትሪያርኩ ልዩ ቪድዮ እና ፎቶ ግራፍ አንሺ እንደሆነ የሚነገረውና ለሳቸውም ከፍተኛ ቀረቤታ እንደነበረው የሚነገርለት ዲያቆን አሁን ደረሰ አቡነ ማቲያስ በሰሜን አሜሪካ ለ10 ቀናት ለጉብኝት በመጡበት ጊዜ ፓስፖርቱ እና ሁሉ መረጃዎቹ ተይዘውበት የነበረ ቢሆንም ወደ ኢትዮጵያ ላለመመለስ እንደጠፋባቸው ተገልጿል።

ምንጮቻችን እንደሚሉት ዲያቆን አሁን ደረሰ አቡነ ማቲያስ ወደ ኢትዮጵያ ሲመለሱ አብሯቸው ያልተመለሰ ሲሆን እስካሁን በምን ዓይነት ምክንያት ጥገኝነት ይጠይቅ አይጠይቅ የታወቀ ነገር የለም። ከፓትርያርኩ ጋር አብረው ከአዲስ አበባ የመጡት ሁሉ ወደ ኢትዮጵያ እስኪመለሱ ድረስ ፓስፖርታቸው ተይዞባቸው እንደነበር የገለጹት ምንጮቹ ዲያቆን አሁንን በምን ምክንያት የሃገር ቤቱን ሲኖዶስ ጥሎ በአሜሪካ ሊቀር እንደቻለ ለማነጋገር እንደሚሞክሩ ቃል ገብተዋል።

[የሳዑዲ ጉዳይ] ይሄ ነው ወገኔ

$
0
0

ከጃ ዘ-ኢትዮጵያ

ይሄ ነው ወንድሜ ይሄ ነው ወገኔ
በመከራ ግዜ ያልሸሸው ከጎኔ
ከንፈር ሳይሆን ትከሻውን ያበደረ
ፊቱን ያላዞረ እጅን የሰደረ
እግሩ እግሬን ሆኖ ክፉ ቀኔን ያሻገረ
እሱ ነው ወገኔ ይሄነው መከታ
ምንም ቀን ቢጨልም ከጎኔ ያልሸሸ የማታ የማታ
ሀበሻ ምቀኛ ሀበሻ ክፉ ነው እያልኩኝ ስናገር
እንደኖህም መርከብ እንደሙሴ በትር
እግሩን ላጣ ወገን እግሩን በማበደር
በስደት በረሀ ወገን የሚያሻግር
ይሄ ነው ሀበሻ እውነት የሰውልጅ ዘር
በችግር ጉዳት ቆሞ ያልገለፈጠ
አይቶ እንዳላየ ዞሮ ያልፈረጠጠ
ይሄ ነው ወገኔ እርዳታውን ስሻ በኔ ያልተለወጠ።
ze ethiopia

የዋሽንግተን ዲሲው የኢትዮጵያ ኢምባሲ አፈ ቀላጤ አቶ ጸሐዬ ደባልቄ ውሸት በጠራራ ፀሐይ ተጋለጠ

$
0
0

ከኢሳያስ ከበደ

በዋሽንግተን ዲሲ የኢትዮጵያ ኢምባሲ አፈ ቀላጤ የሆኑት አቶ ፀሐዬ ደባልቀው በአደባባይ ሲዋሹ እጅ ከፍንጅ ተያዙ። አቶ ጸሐዬ ደባልቀው በጠራራ ፀሐይ ሲዋሹ የተያዙበት መረጃ የወያኔን ላለፉት ሃያ ዓመታት ውሸት በይፋ ያጋለጠና ለስርዓቱም ክስረት መሆኑን የፖለቲካ ተንታኞች እየተናገሩ ነው። ነገሩ እንዲህ ነው – ሰሞኑን በሳዑዲ አረቢያ በኢትዮጵያውያን ወገኖቻችን ላይ እየደረሰ ባለው ስቃይ የተቆጡ ኢትዮጵያውያን በተለያዩ ሃገራትና ከተሞች ሰላማዊ ሰልፍ ሲያደርጉ ቆይተዋል። ኢትዮጵያውያኑ ወያኔን የሚቃወሙ የተለያዩ መፈክሮችን ይዘው እንደነበርም ይታወሳል። ታዲያ ከተደረጉት ሰልፎች መካከል አቶ ጸሐዬ ደባልቄ የተጋለጡበትና ለሥርዓቱም ኪሳራ ነው የተባለለት ጉዳይ በላስቬጋስ እና በዋሽንግተን ዲሲ የተደረጉ ሰልፎች ፎቶ ግራፎች ናቸው። አቶ ጸሐዬ ሃገር ቤት ቴክኖሎጂው ሁሉ በወያኔ አፈና ስለተዘጋ የኢትዮጵያ ህዝብ መረጃውን አያገኝም በሚል በፎቶ ሾፕ እና በቪድዮ ኤዲቲንግ የለመዱትን የውንጀላ ተግባር እዚህም እንዲያው መስሏቸው ትግራይ ኦንላይን በተሰኘ ዌብ ሳይት ላይ በላስ ቬጋስ ኢትዮጵያውያን ይዘውት የወጡትን መፈክር በፎቶ ሾፕ ቀይረው የኢሳያስ አፈወርቂ ፎቶ በማስገባት ሕዝቡን ለማሳሳት ከመሞከራቸውም በላይ የኢሳያስን ፎቶ ግራፍ ያልያዘ ልጅ እንደያዘ አስመስለው በመስራት በሕግ የሚያስጠይቅ የሚያዋርድ ሥራ ሰርተዋል። ይህ የሚያዋርድ ብቻ ሳይሆን በሳዑዲ ባለቁት እና እየተሰቃዩ ባሉት ዜጎች ላይም መቀለድም ጭምር ነው። በላስቬጋሱ ሰልፍ ላይ ኢትዮጵያዊው የያዘው መፈክር በሳዑዲ አረቢያ የኢትዮጵያ ኢምባሲ መዘጋቱን የሚገልጸውን ደብዳቤ ሲሆን አቶ ጸሐዬ በኢሳያስ ፎቶ በመቀየር “ወያኔ በቃን” በሚል ተሰላፊው ኤርትራዊ ወይም የኤርትራ ደጋፊ ለማስመስል ሲሞክሩ ተዋርደዋል። ሌላው ውሸታቸው ይህን ፎቶ ልክ ዋሽንግተን ዲሲ ላይ እንደተደረገ አድርገው ሲያቀርቡት ፎቶ ግራፉ ግን የተነሳው ላስቬጋስ ላይ መሆኑ በጠራራ ጸሐይ የወያኔን ውሸት አጋልጦ ስርዓቱን ሸንካላ የፕሮፓጋንዳ ባለሙያዎች እንዳሉት አሳይቶናል። ሁለቱንም ፎቶ ግራፎች ይመልከቱና በወያኔዎች ይሳቁባቸው፦

አቶ ጸሐዬ በፎቶ ሾፕ የሠሩት ፎቶ፦
abet weshet
ትክክለኛው በላስቬጋስ የተደረገው የሰላማዊ ሰልፍ ፎቶ
Tsehaye Debalkew

“እኔ ራሴ ስድስት ያበዱ ሴቶችን ይዤ መጥቻለሁ..”ራውዳ ጀማል –ከሳዑዲ ተመላሽ ኢትዮጵያዊት (ቃለ ምልልስ)

$
0
0

በሃገር ቤት እየታተመ የሚወጣው አዲስ አድማስ ጋዜጣ ከሳዑዲ አረቢያ ወደ ሃገራቸው ከተመለሱ ኢትዮጵያውያን ጋር ቃለ ምልልስ አድርጓል። ቃለ ምልልሱ ዘ-ሐበሻ ከዚህ ቀደም ትዘግባቸው የነበሩ የሳዑዲ ሕይወቶችን የሚያጠናክሩ በመሆናቸው ጋዜጠኛ አበባየሁ ገበያው ያደረገችውን ቃለምልልስ ለአንባቢዎቻችን እንደወረደ ይኸው፦
ራውዳ ጀማል ትባላለች፡፡ የሃያ ዓመት ወጣት ናት፡፡ ስለራስዋም ሆነ በሳኡዲ ስላሉ ኢትዮጵያውያን ወቅታዊ ሁኔታ ስታወራ እያለቀሰችና እየተወራጨች ነው፡፡ ለማነጋገር ስቀርባት “ወንድ ከሆናችሁ ጋዜጠኞች ነን፣ የህዝብ አፍ ነን ካላችሁ፤ እዚህ ተቀምጣችሁ፣ “ሁለት ሰው ሞተ” እያላችሁ ከምታቅራሩ ሳኡዲ ሂዱና በየቀኑ ሁለት ሶስት ሰው የሚሞትበትን እልቂት ተመልከቱ፣ “ሰዎቹን ምን እየሰራችሁ ነው?” ብላችሁም ጠይቁልን” አለችኝ። መቅረፀ ድምፄን ሶስት አራት ጊዜ ያስጠፋችኝ ቢሆንም በመጨረሻ ግን ለቃለ ምልልስ ፈቃደኛ ሆነችልኝ፡፡
Rawda Jemal
ስንት ዓመት ቆይተሽ መምጣትሽ ነው?
ከሁለት ዓመት በኋላ ነው የመጣሁት፡፡ እስከ አስረኛ ክፍል የተማርኩት አዲስ አበባ ቢሆንም፤ የኮምቦልቻ ልጅ ነኝ፡፡
እንዴት ነበር የሄድሽው?
በፓስፖርት… በኮንትራት ነበር የሄድኩት … ካላስ! የሰውየው ልጆች ግን “የማይሆን” ፊልም ተመልከቺ እያሉ ያስቸግሩኝ ነበር፡፡ ሲመረኝ ጠፍቼ ወጣሁ፡፡ ከዚያም ከጓደኞቼ ጋር በነፃነት ቤት ተከራይተን እየኖርን፣ በ1800 ሪያል ተቀጥሬ መስራት ጀመርኩኝ፡፡ ቤተሰቤንም ገንዘብ እየላኩ እረዳ ነበር፡፡
ወደ አገርሽ እንዴት ተመለስሽ?
ውጡ ሲባል… ረብሻ ሲነሳ.. ጓደኞቻችን ሲሞቱ.. ሲደፈሩብን.. ‘ድሮም ስደተኛ ክብር የለውም’ ብዬ ተመልሼ መጣሁ..ከሚገሉኝ ከሚያበለሻሹኝ ብዬ እጄን ሰጠሁ፡፡ ብዙ ኢትዮጵውያኖች ችግር ላይ ናቸው.. እባካችሁ ድረሱላቸው፡፡ ብርዱም ፀሃዩም ሲፈራረቅባቸው.. ያሳዝናሉ፡፡ ብዙ ያልመጡ አሉ፤ መምጣት እየፈለጉ፡፡ ስቃይ ላይ ናቸው፡፡ እኔ አሁን አስራ ሶስት ቀን ታስሬ ነው የመጣሁት፡፡ እስቲ ስለ እስሩ ንገሪኝ … ሁለት ቀን ያለ ምግብ ያለ ውሃ ነው የታሰርነው። ከዛ በኋላ ግን ጥሩ ምግብ ሰጥተውናል፣ ጥሩ መኝታም አግኝተናል፡፡ ብዙዎቹ ግን ከእኛ የባሰ ችግር ላይ ናቸው፡፡ መጠለያ ያላገኙ አሉ… ኤምባሲያችንም አይሰማም እንጂ ስንት ጊዜ ደውለን ተናግረናል መሰለሽ፡፡ ግን የሚሰማ የለም፡፡ ከአገራችን ውጡ ካሉ በኋላ ትዕግስት ያጡና መልሰው ይዩዙናል፡፡ በዛን ጊዜ አበሻው፣ ሻንዛ/ጩቤ ይመዛል፡፡ ፖሊስ ራሱን ለማዳን ይተኩሳል። እኔ እንደውም ደህና ነኝ፤ እዛ ላሉት ድረሱላቸው። በምድረ ዱርዬ እየተደፈሩ ነው ያሉት /ለቅሶ/ ስንት ህፃናት አሉ የሚሞቱ፣ የሚታመሙ፡፡ ስንመጣ ደሞ፤ ሻንጣ አትያዙ ተብለን ተመናጭቀን…በጥፊ ተመትተን..መከራችንን በልተናል፡፡
ወንዶችና ሴቶች ለብቻ ነበር የተቀመጣችሁት?
የተቀመጣችሁት አትበይ! የታሰራችሁት በይ፡፡ … የሴት እስር ቤት ለብቻው ነው በሴቶችና በህፃናት ለቅሶ የተሞላ ነው፡፡ እኔ ራሴ ስድስት ያበዱ ሴቶችን ይዤ መጥቻለሁ…/ለቅሶ/
አሁን ቤተሰብ እየጠበቅሽ ነው?
ነበረ ግን ሻንጣዬ ጠፋብኝ፡፡ በርግጥ ጤነኛ ሆኖ መምጣትም ቀላል አይደለም፡፡ እዛ ያሉትን ጥለናቸው ስንመጣ እያለቀስን ነው፡፡ እስር ቤቱ ውስጥ አንድ እርጉዝ ሞታብናለች፡፡ እዛው እስር ቤት እያለን ምጥዋ መጣ፤ ግን የህክምና እርዳታ ባለማግኘትዋ ሞተች፡፡
እስር ቤት ያሉት ምን ያህል ይሆናሉ?
ሰማኒያ ክፍል አለ..በየክፍሉ ስልሳ አምስት ስልሳ አምስት ሰው ነው ያለው፡፡ መካሲመሺ እስር ቤት ይባላል፡፡ የወንድና የሴት እስር ቤት የተራራቀ ነው፡፡ በጣም ረጅም ከመሆኑ የተነሳ በመኪና እንጂ በእግር አይሞከርም፡፡ በአሁኑ ሰዓት በከተማው ያለው እስር ቤት ሞልቶ የመዝናኛና የስብሰባ አዳራሹን ሁሉ እስር
ቤት አድርገውታል፡፡ የተደፈሩት የሞቱት..ሴቶች ብዙ ናቸው፡፡ አንዷን እርጉዝ ለሶስት ሲደፍሯት ሞታለች፡፡
የሌሎች አገር ስደተኞችም እየወጡ ነው ተብሏል…
አዎ፡፡ ኢትዮጵያዊው ከበደሉ ብዛት የተነሳ እየተናነቀው እኮ ነው ግጭቱ የሚከረው፡፡
ሚስቱን እህቱን ከእጁ መንትፈው ሊወስዱበት ሲሉ ነው ጦርነት የሚነሳው፡፡ አበሻ ወንድ እየሞተ ያለው ‹‹ሴቶቻችንን አትንኩብን..›› ስለሚል እኮ ነው፡፡ ኤምባሲው ሊደርስላቸው ይገባል፡፡

“ነብሰ ጡሯን አስገድደው ሲደፍሯት ሞተች..”–ፀጋ ኪዳኔ (ከሳዑዲ ተመላሽ ኢትዮጵያዊት –ቃለምልልስ)

$
0
0

ዛሬ በአዲስ አበባ ታትሞ የወጣው አዲስ አድማስ ጋዜጣ ከሳዑዲ አረቢያ ተመላሽ ከሆኑ ኢትዮጵያውያን መካከል የተወሰኑትን በጋዜጠኛ አበባየሁ ገበያው በኩል አነጋግሯል። ዘ-ሐበሻ ለግንዛቤ ይረዳ ዘንድ እንደወረደ አስተናግዳዋለች፦
Tsega Kidane
ስምሽ ማን ነው?
ፀጋ ኪዳኔ ገብረኪዳን
ምን እየጠበቅሽ ነው?
ዘመድ አለችኝ አዲስ አበባ የምትኖር፤ እስዋ እስክትመጣ እየጠበቅሁ ነው፡፡
ሳኡዲ ምን ያህል ጊዜ ቆየሽ?
ከአንድ ዓመት ቆይታ በኋላ ነው ከሪያድ/ሞንፋ የመጣሁት፡፡ ከኢትዮጵያ ስሄድ በኮንትራት ቢሆንም በባህር ከሄዱት ስደተኞች የተለየ ክብር አላገኘሁም፡፡ ጭቅጭቅ፣ ስድብና ድብደባ ሲበዛብኝ ከተቀጠርኩበት ቤት በስምንተኛ ወሬ ወጥቼ ጠፋሁ፡፡ የሄድኩት ለአንድ ስራ ብቻ ተዋውዬ ነበር። የምተኛው ግን ከሁለት ሰዓት አይበልጥም ነበር፡፡ ሥራ ብቻ ነው 24 ሰዓት!
እስቲ ስለደረሰብሽ ችግር በዝርዝር ንገሪኝ..
በ700 ሪያድ ተቀጥሬ ነበር ከዚህ የሄድኩት፡፡ አሰሪዬ ቤት አራት ትላልቅ ወንድ ልጆች አሉዋት። የእህትዋ ልጆችም እዚያው ነው የሚኖሩት፡፡ ‹‹ወሲብ ካልፈፀምን..›› ብለው ያስቸግራሉ፡፡ በጣም ተሰቃየሁ፡፡ ከአቅሜ በላይ … ለህይወቴ በጣም አስፈሪ….ሲሆንብኝ ወጣሁ፡፡ ከአቅሜ በላይ ስትይ …
ልጆቹ ወሲብ ካልፈፀምን ብለው አሻፈረኝ ስላቸው፣ “በቢላ እናርድሻለን” እያሉ ያስፈራሩኝ ነበር፡፡ እምነቴን እንድቀይር ሁሉ ይፈልጋሉ። አፈር ድሜ በላሁ፡፡ ሰርቼ ለፍቼ … በዚያ ላይ ነፃነት አልነበረኝም፡፡ ወገቤ፣ ዓይኔ ታመመ፡፡ እነሱ እኮ ሃያ አራት ሰዓት እየበሉ እየጠጡ ነው፡፡ በዚያ ላይ በእጅሽ ላይ ስልክ ማየት አይፈልጉም፡፡ ሁሉ ነገር ሲያንገፈግፈኝ ሁለት ወር የሰራሁበትን ገንዘብ ጥዬ ወጣሁ፡፡ ከዛ ኤጀንሲው ለሌላ ሰው ሸጠኝ፤ በአስር ሺህ ሪያድ፡፡ እዚያም ግን አልተመቸኝም። ስራው ሃያ አራት ሰዓት ነበር፡፡ አምስት ሰው እንኳን የማይችለው ስራ ነበር፡፡ አንድ ኩንታል ሊጥ አብኩቼ፣ ለሱቅ የሚሸጡት ብስኩት ጠብሼ፣ ሰባት መቶ ሪያል ነበር የሚከፈለኝ፡፡ ሁለት ወር ሙሉ እንደምንም ድምጼን አጥፍቼ ሰራሁ… በእንቅልፍ እጦት ልወድቅ እየተንገታገትኩ፡፡ እፊታቸው ላይ ግን ደስተኛ እመስል ነበር፡፡ ሰውነቴ እየመነመነ መጣ፡፡ ይሄኔ ድጋሚ ለመጥፋት ተዘጋጀሁ፡፡
“ለሌላ ሰው ሸጠኝ” ያልሽው … ኢትዮጵያዊ ነው?
/እንባዋ እየፈሰሰ/አረብ ነው፡፡ ወደ ሳኡዲ ከላከኝ ኤጄንሲ ጋር አብሮ ይሰራል፡፡ የረመዳን ጊዜ ደግሞ ሱቃቸው ወሰዱኝ፤ የአንድ ሰዓት መንገድ ተጉዞ ሌላ ቤት አላቸው፡፡ እዛ ይዘውኝ ሲሄዱ ስራ ይቀልልኛል ብዬ ነበር፡፡ … ግን የባሰ ሆነብኝ፡፡ ለካ ጓደኞቻችን ወደው አይደለም ራሳቸውን የሚያጠፉት፤ አብደው ጨርቃቸውን ጥለው በየጎዳውና የወጡትና መንገዱ የወደቁት … የወገብና የአእምሮ በሽተኞች የሆኑት? “ምነው እናቴ ስትወልጅኝ በመሃፀንሽ ውስጥ ደም ሆኜ በቀረሁ? እናቴ እባክሽ መልሰሽ ዋጪኝ” አልኩኝ፡፡ ራሴንና ቤተሰቤን ልረዳ ስንገታገት ከፊታቸው ድፍት ብል እኮ … እንደሰው ከቆጠሩኝ … ሬሳዬን ለእናቴ ይልኩላት ይሆናል፡፡ ያለዚያ ግን የሀገራቸው መንግስት አውጥቶ ይቀብረኛል፡፡ ከዚያ ሁሉ በፊት ጠፍቼ መውጣት እንዳለብኝ አሰብኩ፡፡ አንድ ቀን ረመዳን ካፈጠሩ በኋላ ቤተሰቡ ተሰብስቦ ሊዝናኑ ወጡ፡፡ ደስ አለኝ፡፡ ቶሎ ብዬ የሴትየዋን ሙሉ ልብስ ለብሼ፣ ሽፍንፍን ብዬ ወጣሁ፡፡
ሻንጣ ምናምን ሳትይዢ?
ባዶ እጄን ነው የወጣሁት፡፡ የሰራሁበት ገንዘብ እንኳን በእጄ የለም፡፡ በቃ ዝም ብዬ ወጣሁ፡፡ ፓኪስታናዊ የታክሲ ሾፌር አገኘሁ፡፡ ‹‹ምን ሆንሽ?›› ብሎ ሲጠይቀኝ በዝርዝር ነገርኩት፤ አዘነ፡፡ ‹‹ሪያድ የሀበሻ ሃገር ነው፤ ብዙ ኢትዮጵያዊ አለ›› ብሎ እዛ (በነፃ) ወሰደኝ፡፡ ብዙ ኢትዮጵያውያን አገኘሁ፡፡ እዚያ መኖር ጀመርሽ ማለት ነው?ሳያቸው በጣም ነው ያለቀስኩት፡፡ አገሬ የገባሁ ይመስል..መሬት ሁሉ ስሚያለሁ፡፡ ከኢትዮጵያ በባህር (በህገወጥ መንገድ) የመጡ ሴቶች ነበሩ። ከእነሱ ጋር አንድ ቤት በስድስት መቶ ሪያድ ለስድስት ወር ተከራይተን አብረን እየኖርን እንሰራ ጀመር፡፡
ቤቱን ለስንት ተከራያችሁ?
አስር ነበርን፡፡ ሁለት ወር እንደሰራሁ ግን በአካባቢው ግጭት ተነሳ፡፡ እግሬ አውጪኝ ብለን በየፊናችን ተበታተንን፡፡
ምን ዓይነት ግጭት?
መንግስት የሌለበት አገር ይመስል ጐረምሶች በር እያንኳኩ በሽጉጥ፣ በካራ፣ ሰው መግደል ጀመሩ፡፡ ስለዚህ ‹‹እጃችንን እንስጥ›› ብለን ተማከርን፡፡ ሌላው ችግር ፖሊስ፤ ትዳር መስርተው የሚኖሩትን የአበሻ ወንዶች እየወሰደ፣ ሴቶችን ለብቻቸው ይተዋቸው ነበር፡፡ በቤቱ ወንድ አለመኖሩን የተገነዘበ የአገሩ ዱርዬዎች (እንኳን ለአበሻው ለመንግስትም ልባቸው ያበጠ ነው) ሴትዋን ለአራትና ለአምስት እየሆኑ መድፈር ያዙ፡፡ ከእኛ ጎን የነበሩትን ሲያሰቃይዋቸው አይተናል፡፡ ወንዶቹን ፖሊስ ሲወስዳቸው ጎረምሶቹ ተከትለው ይገቡና ሴቶቹን መጫወቻ ያደርጓቸዋል/ለቅሶ/፡፡ አንድ ያየሁትን ልንገርሽ../ረጅም ትንፋሽ/ እነዚህ ጐረምሶች…ሶስት ሴቶች ያሉበት ክፍል ውስጥ ገብተው ለሰባት ደፈሯቸው፡፡ /ማውራት አልቻለችም፤ ሳግና እንባዋ እያቋረጣት/..ከሶስቱ አንዷ የሰባት ወር ነፍሰጡር ነበረች፤ ሲገናኝዋት ሞተች፡፡ አንዷን ደግሞ ለሰባት ደፈሯትና ገድለው ጥለዋት ሊወጡ ሲሉ ሽርጣ/ፖሊስ መጣ፡፡ ከፖሊስ ጋር ተኩስ ገጥመው እርስ በርስ ተገዳደሉ፡፡ የሀበሻ ወንድ ከእህቱ ወይንም ከሚስቱ ሊለዩት ሲመጡ አልለይም ይልና ይገደላል፤ ይደበደባል … በቃ እልቂት ይሆናል፡፡ አዲስ አበባ ብለሽ ካራ ቆሬ እንደምትይው..ሪያድ ብለሽ ሞንፋ የሚባል አካባቢ በርካታ አበሾች ይኖራሉ፡፡ እኔ እንኳን የማውቀው … ከአምስት በላይ ሴቶች እንደተገደሉ ነው፡፡ መላ አካላቸውን ቆራርጠው ነው የጣሏቸው፡፡ ግን ይሄ ሁሉ መከራ ምን አድርገን ነው?
አንቺ እንዴት መጣሽ ወደ አገርሽ?
እጄን ሰጠኋ፡፡ አሰሪዬ ‹‹የት ልትሄጂ ነው?›› ብላ ስትጠይቀኝ፡፡ ‹‹አንድ ጓደኛዬ ልትወልድ ነውና ልጠይቃት ..›› ብዬ የሰራሁበትንም ሳልቀበል ወጣሁ፡፡ ምክንያቱም ብትገለኝስ ብዬ ፈራሁ፡፡ አብዛኛው አበሻ ከስራ ወደቤቱ ሲሄድ እየተያዘ ነው የሚመጣው፡፡ የሰራበትን የለፋበትን ሳይዝ ባዶ እጁን፡፡ እና እኛም ነገሩ ስላስፈራን እጃችንን ሰጠን። በቃ እኔም ወደ እዚህ መጣሁ፡፡
ዛሬ ላይ ሆነሽ ስታስቢው ወደዛ በመሄድሽ ምን ይሰማሻል?
መጀመሪያ ከዚህ ስሄድ በጣም ደስ ብሎኝ ነበር፤ የራሴንና የቤተሰቤን ህይወት ላሻሽል እንደሆነ ተስፋ በማድረግ፡፡ ከዛ በኋላ ግን ከስራው ብዛት የተነሳ ከጥቅም ውጪ ልሆን ነው ብዬ እጅግ አምርሬ አለቅስ ነበር፡፡ በጣም ስጋት ያዘኝ፡፡ ግን ከሞት ተርፌ ወደዚህ ስመጣ አምላኬን አመሰገንኩ፡፡
ቤተሰብሽ መምጣትሽን አውቀዋል?
አላወቁም፡፡ ምን እያሰቡ ይሆን? ይሄን ሁሉ ነገር እየሰሙ፡፡ እናቴ መንገድ መንገድ እያየች ይሆናል፡፡ ደሞ ከእኛ አካባቢ ልጆች ብዙ የሞቱ አሉ፡፡..አሁን እኔ ራሴ የሁለት ሰው መርዶ ይዤ መጥቻለሁ፡፡ እናቴም ሰው ሲመጣ ‹‹ልጄን አይታችኋል?›› ትል ይሆናል፡፡ እኔስ መጣሁ..በረሃ ላይ ተደፍተው ለመምጣት ወረፋ እየተጠባበቁ ያሉ ህጻናትና ሴቶች ብዙ ናቸው፡፡ እዚህ የመጣነው እኮ ግማሽ አንሞላም፡፡ በሳኡዲ የኢትዮጵያውያን እንባ ያሳዝንሻል፡፡ ብዙዎቹ በሃዘን ላይ ናቸው፤ ድረሱላቸው፡፡


“አንድ ጊዜ ሆድ ብሶኝ ራሴን ለማጥፋት ሞክሬ ነበር”–ከሳዑዲ ተመላሿ ሃያት አህመድ (ቃለምልልስ)

$
0
0

ከዚህ በፊት ባቀረብናቸው ሁለት ዜናዎች ከሳዑዲ አረቢያ ስቃይ ተርፈው ለሃገራቸው መሬት ከበቁት ኢትዮጵያውያን መካከል የሁለቱን ከአዲስ አድማስ ጋዜጠና አበባየሁ ገበየሁ ጋር ያደረጉትን ቃለምልልስ ማስነበባችን ይታወሳል። አሁንም የምናቀርብላችሁ ሓያት አህመድ የተባለችውን ከሰሞኑ ለሃገሯ ምድር የበቃችውን እህታችንን ቃለምልልስ ይሆናል – እንደወረደ ይኸው፦
Sayat Ahemed
ስምሽን ንገሪኝ..?
ሀያት አህመድ
እስቲ አካሄድሽን ንገሪኝ …
ከደሴ ነው በኤጀንሲ የሄድኩት፡፡ የምሰራው በጠለብ/በህጋዊ መንገድ ነበር፡፡ ሰዎቹ ሳይመቹኝ ሲቀሩ..ብዙ ጓደኞቻችን ችግር ሲደርስባቸው ሳይ፣ ስልካችንን ቀምተው ቤተሰቦቻችን በሃሳብ ሲያልቁ፣ እኔም ነገሩ ስላልተመቸኝ ጥዬ ጠፋሁ፡፡ ከዛም በሃጂና ኡምራ የሄድኩ አስመስዬ ተቀጥሬ መስራት ጀመርኩ፡፡
በጠለብ ስንት ጊዜ ሰራሽ?
ሶስት ወር ነው የሰራሁት፡፡
አሰሪዎችስ ቤት የሚደርስብሽ ችግር ምን ነበር?
በቤት ውስጥ ያሉ ወንዶች ያስቸግሩኝ ነበር፤ አስገድዶ ለመድፈር ይተናነቁኛል፡፡ አሰሪዬ በስራዬ አትደሰትም፣ ያጠብኩትን ነገር እንደገና እጠቢ ትለኛለች፡፡
“የኢትዮጵያ ሰራተኞች ሞያ የላቸውም፣ “ሞዴስ እንኳን በአግባቡ መጠቀም አይችሉም፣ በዚያ ላይ ወንዶቻችንን ያባልጋሉ” የሚል ክስ ከሳኡዲ ሴቶች ይሰማል፡፡ አንቺ ምን ትያለሽ?
በጭራሽ! እኛ ደልቶን ይሄን ልናስብ? አንገታችንን ቀና አድርገን እንኳን ለመሄድ እንቸገራለን እኮ፡፡ እዛ ቦታ ላይ እኛን ብታይ ኢትዮጵያዊነት ያስጠላሻል፡፡ አለባበሳችን ምንድን ነው፣ ሁኔታችንስ፣ ኑሮዋችንስ..እኛ የእነሱን ባል የምናባልግ ምን አምሮብን፣ እንዴት ሆነን ነው? እኛን እኮ ይጠየፉናል፡፡ በምን አንገታችን ቀና ብለን ነው የእነሱን ወንዶች የምናባልገው? እኛ እኮ ለህይወታችን እየሰጋን ነው… እያንዳንዷን ቀን የምናሳልፈው፡፡ በርግጥ የገጠር ልጆችም ይሄዳሉ። እንግዲህ በንፅህና የሚታሙት እነሱ ናቸው፡፡ ግን ስንቱን አእምሮውን አሳጡት…. ወይኔ!!..አሁን ስንመጣ እንኳን ጅዳ ኤርፖርት ውስጥ ሰባት ያበዱ ልጆችን አይቻለሁ፡፡ ‹‹ይዛችኋቸው ሂዱ›› ሲሉን ነበር፤ እንዴት አድርገን እንይዛቸዋለን? ጥለናቸው ነው የመጣን፡፡ አይ ዜጎቻችን! እየቀወሱ፣ እየተደፈሩ፣ እየተደበደቡ፣ እየተጣሉ ነው ሜዳ ላይ ….ተመልካች አጥተው፡፡
ጣትሽ ላይ የጋብቻ ቀለበት አያለሁ … ባለትዳር ነሽ?
ፈትቻለሁ፡፡ የአስር ዓመትና የስምንት ዓመት ልጆች አሉኝ፡፡ እነሱን ላሳድግ ብዬ ነው በሰው አገር የተንገላታሁት፡፡ ገንዘብ እልክ ነበር፡፡ ሆኖም እኔም አልተለወጥኩም፤ ለልጆቼም አልሞላልኝም፡፡ አንድ ጊዜ ሆድ ብሶኝ ራሴን ለማጥፋት ሞክሬ ነበር፡፡ ታውቂያለሽ… ልጆቼ በዓይን በዓይኔ መጡብኝና … ከድርጊቴ ታቀብኩ፡፡
አይኔ እንቅልፍ ካጣ ስንት ጊዜው ሆነ መሰለሽ… አይኔ ስር ጥቁር ብሎ የምታይው፣ የበለዘ የሚመስለው እኮ በእንቅልፍ እጦት የተፈጠረብኝ ነው፡፡ ጀርባዬን ያመኛል፡፡ ብዙ ሰዓት የምቆምበት እግሬንም እጅግ ታምሚያለሁ፡፡ አሁን ለትንሽ ጊዜ ማገገም አለብኝ፡፡
ጂዳ ኤርፖርት ወደ ኢትዮጵያ ለመምጣት የሚጠባበቁ በርካታ ኢትዮጵያዊያን አሉ ይባላል…?
በጣም ብዙ እንጂ! ‘ኢትዮጵያዊ ሁሉ አገር ነቅሎ ነው እንዴ የወጣው ብዬ ተደንቄያለሁ፡፡ በጣም ያዘንኩት ግን ወደዚህ ስመጣ ኤርፖርት ሰባት ያበዱ ልጆች ስመለከት ነው፡፡
እዛ ያለው ኤምባሲያችን እንዴት ወደ አገራቸው አይመልሳቸውም?
‹‹እህ›› ብሎ ችግራቸውን የሚያደምጣቸው ይፈልጋሉ፡፡ እስቲ አስቢው…ሰባት ሴቶች አብደው አይቻለሁ፤ በአይኔ በብረቱ፡፡ አንዷ ልጅዋ ሞታባት (በረሃብ ነው) የቀወሰችው፡፡ ስድስቱ ደግሞ በስራ ቦታቸው ቀውሰው፣ አሰሪዎቻቸው ናቸው አምጥተው የጣልዋቸው፡፡ የምናየው ነገር ሁሉ ለዓይን ይዘገንናል፡፡
ከዕረፍት በኋላ ምን ልትሰሪ አቀድሽ…?
አሁን ጤንነት አይሰማኝም፤ ካገገምኩ በኋላ እንግዲህ … እንጃ ምን እንደምሰራ፡፡ አንድ ዓመት ከሶስት ወር ተቀምጬ ነው የመጣሁት፡፡ ከአስርና አስራ አምስት ዓመት በላይ የኖሩትም ‹‹ምንድነው የምንሰራው..›› የሚል ነው ጥያቄያቸው፡፡ ብዙ ጊዜ ኖረው ቢመጡም ምንም የያዙት ነገር የላቸውም፡፡ በጣም ያሳሰበኝ እሱ ነው፡፡
ከአሁን በኋላ ወደ ሳኡዲ የመመለስ ሃሳብ አለሽ?
አላህ ያውቃል፡፡

ታላቅ ሰላማዊ ሰልፍ በፍራንክፈርት ከተማ (Germany)

$
0
0

በፍራንክፈርት ከተማ የሚደረገው ሰላማዊ ሰልፍ ዲሴምበር 2.2013 ከጠዋቱ 10 ሰአት ሲሆን መነሻው ፍራንክፈርት ዋና ባቡር ጣቢያ ነው

ድምፅ ላጡ ወገኖቻችን ድምፃችንን እናሰማ

Frunkfurt

ቅድሚያ ወያኔን ነው!! በ አንተነህ ሽፈራው

$
0
0

ቅድሚያ ወያኔን ነው!!

 

ደላላው ወያኔ ለዐረብ አሸሻጩ፣
ገጠር ድረስ ሄዶ ትዳር እያፋቱ – እርስ በርስ እያጋጩ፣
አዲስ ጎጆ አፍርሶ “ሀ” ብሎ ከንጭጩ::
በቀቢጠ ተስፋ ልብን አንጠልጥሎ፣
የራበውን አንጀት በመና ደልሎ፣
ለዐረብ ዳረጋቸው ጉቦ ተቀብሎ::
በዐረብ ሰላጤ ብሎም በቀይ-ባሕር፣
በሲና በረሃ በጭካኔ ምድር፣
የገጠር ሙሽራ ሴት ወንድ አልቀረ፣
ተማሪው ምሩቁ የተመራመረ፣
ያልፍልኛል ብሎ ስንቱ ወጦ የቀረ::
ዐረብ ግፍ አይፈራ ስብዕና የለው – - – ጭራሽ አረመኔ፣
ስንቱን ከፎቅ ጥለው ገሎ በጭካኔ፣
ስንቱን እህል ነፍገው ገደሉ በጠኔ፣
እግዜር ይክተታቸው ከሲዖል ኩነኔ::
ተልዕኮው ቀላል ነው ብዙም ሚስጢር የለው፣
ይህም ዘዴ ሆኖ ያው እንደልማዱ ትውልድ/ዘር ማጥፋቱ ነው፣
ለዚህ እርኩስ ስራው ጥማድ በሬ አይበቃው – - – ተመኑ ብዙ ነው፣
ከዚህም ለመላኪያ ከዚያም ለአባይ ግድብ የሚሞጨልፈው፣
ወገኔ ተረዳ መንታ መንገዱን ተው፣
የዐረብ ጠላትነት (በሶማሌ ወጉን) ከጥንትም ያለ ነው፣
ከአገር ነቅሎ መጣል የባንዳን ጥርቅም ቅድሚያ ወያኔን ነው (2)!!

 
አንተነህ ሽፈራው/23 Nov 2013
መታሰቢያነቷ በዐረብ አገር በግፍ ለተገደሉ፣
ክብራቸው በተለያዩ መንገዶች ለተደፈሩና
አሁንም ለሚንገላቱ ኢትዮጵያውያን ወገኖቼ
ትሁንልኝ!!

 

Pen

የብሔራዊ ዕርቅ ጥያቄና ፈተናዎቹ በኢትዮጵያ በዳዊት ተሾመ

$
0
0

ከደርግ የ17 አመታት የአገዛዝ ውደቀት በኋላ በኢትዮጵያ የፖለቲካ ኃይሎች በስፋት ሲንጸባረቁ ከነበሩ ጥያቄዎች መካከል የብሔራዊ ዕርቅ ጥያቄ ዋነኛው ነው::

National recocilationበዚህ ወቅት ውስጥ ለብሔራዊ ዕርቅ ጥያቄ በፖለቲካ ኃይሎች የቀረቡት የመፍትሔ ሃሳቦች የተለያዩ ቢሆንም የመፍትሔ ሃሳቦቹ የሚመነጩት ግን በዋናነት ከሁለት ተገዳዳሪ አስተሳሰቦች ነው:: አንደኛው አስተሳሰብ የሚያጠነጥነው የብሔራዊ ዕርቅ ጥያቄው የሚካትተው ከኢትዮጵያ ዘመናዊ የሃገር ግንባታ ጋር ተያይዞ የተፈፀሙ ታሪካዊ ኢ-ፍትሃዊነትንና በደሎችን እንዲሁም በያ ትውልድ ውስጥ የተፈፀሙ መጠፋፋትን አካቶ ሁሉን-አካታች መድረክ በማዘጋጀት ያለፈውን በደሎች ዕውቅና በመስጠት በፖለቲካ ሊህቃን መካከል መግባባትን ማስፈንን ነው:: ሁለተኛው አስተሳሰብ የብሔራዊ ዕርቅ ጥያቄን የሚመለከተው ኢትዮጵያን እንደ ሀገር በአዲስ መሰረት ላይ የመገንባት ሂደት አድርጎ ነው:: ይህም ማለት የብሔራዊ ዕርቅ ጥያቄ የሚያቅፈው ሁሉንም አይነት ማለትም ብሔር፣ ሃይማኖት እንዲሁም መደብ ላይ መሰረት ያደረገ ኢ-ፍትሃዊነትና መገለልን ከኢትዮጵያ ዘመናዊ የሃገር ግንባታ ጀምሮ የኢህአዴግን የአገዛዝንም የሚያካትት ነው::  ...የብሔራዊ ዕርቅ ጥያቄና ፈተናዎቹ በኢትዮጵያ….

Download (PDF, 317KB)

 

በሳዑዲ አረቢያ አልቃሲም ከተማ አፈሳ ተጀመረ

$
0
0

Saudicry
(ዘ-ሐበሻ) ከሳዑዲ አረቢያ 13 ግዛቶች ውስጥ በሰው ብዛት 7ኛ እንደሆነች በሚነገርላት አል ቃሲም ከተማ ስደተኞችን ማፈስ ተጀመረ። ከትናንት ጀምሮ ፖሊስ በየቤቱ እየሰበረ በመግባት ስደተኞችን እያፈሰ መሆኑን ከአካባቢው የዓይን እማኞች ለዘ-ሐበሻ በላኩት መረጃ ዘገበዋል።

ከዚህ ቀደም በሪያድና በመካ በርካታ ኢትዮጵያውያን ሞት፣ ለድብደባ፣ ለዝርፊያና ለአስገድዶ መደፈር ያበቃው ስደተኞችን የማባረሩ ተግባር ወደ አልቃሲም ከተማ ተሸጋግሮ ቁጥራቸው በውል ያልታወቀ በርካታ ኢትዮጵያውን ታስረዋል። ፖሊሶች ካለምንም ማስጠንቀቂያ ቤታቸውን ሰብረው በመግባት በተለይ በሴቶቻችን ላይ ጉዳት እያደረሱ እንደሚገኝ የደረሰን መረጃ ያመለክታል።

በሳዑዲ አረቢያ ሕጋዊ የመኖሪያ ፈቃድ የሌላቸውን ለማስወጣት በሚል የተጀመረው ይኸው የአፈሳ ተግባር ከኢትዮጵያውያን ውጭ ሌሎችንም ሃገራት የሚመለከት ቢሆንም በኢትዮጵያኑ ላይ የሚደርሰው ጥቃት ግን ለየት ያለ ነው። ሰርተው ያፈሩትን ንብረት እየተዘረፉ የሚገኙት እነዚሁ ኢትዮጵያውያን እቃቸውን ሸጠው እንዳይጨርሱ በፖሊስ ስለማይጠበቁ ወደ እስር ቤት የሚጓዙት ካለምንም ንብረት ነው።

በአልቃሲም ከተማ በተጀመረው አፈሳ የሰብአዊ መብት ጥሰቶች እየተፈጸሙ ነው ያሉት የዘ-ሐበሻ ዘጋቢዎች ይህ ስደተኞችን የማሳደድ ተግባር በ13ቱም የሳዑዲ ግዛቶች ይቀጥላል ተብሏል። እንደደረሰን መረጃ ከሆነ በአል ቃሲም ከተማ የመኖሪያ ወረቀት ለሌላቸው ወገኖች ቤት ያከራዩ ሰዎች ይቀጣሉ።

Viewing all 15006 articles
Browse latest View live