Quantcast
Channel: Ethiopian News | ዘ-ሐበሻ | Latest News Provider | News For All
Viewing all 15006 articles
Browse latest View live

በጎንደር የቤት ውስጥ መቀመጥ አድማ ተጀመረ |ዛሬ ምንም ዓይነት እንቅስቃሴ የለም

$
0
0

Zehabesha-News.jpg

(ዘ-ሐበሻ) የጎንደር ሕዝብ በዛሬው ዕለት የቤት ውስጥ የመቀመጥ አድማውን በተሳካ ሁኔታ እያካሄደ እንደሚገኝ ከስፍራው የተገኙ መረጃዎች አመለከቱ::

በጎንደር ዛሬ ጠዋት የቤተክርስቲያን መሳለም እንስቃሴ ብቻ የነበረ ሲሆን ከዚያ በኋላ ሱቆችም ሆኑ የመጓጓዣ አገለግሎቶች ቆመው ውለዋል:: በተለይም አንዳንድ ባጃጆች እና ታክሲዎች ስራ ለመጀመር ሞክረው የነበረ ቢሆንም ከሕዝቡ በተሰጣቸው ማስጠንቀቂያ ሁሉም ቤት ውስጥ መዋሉ ተገልጿል:: የመዝናኛ ቤቶች በጠቅላላ ዝግ ናቸው::

በጎንደር ዛሬ አንዳችም የንግድ እንቅስቃሴ እንደሌለ; በአንጻሩ የትግራይ ነፃ አውጪ ድርጅት ወታደሮች በከተማዋ በመኪና እያንጃበቡ እንደሚገኙ የአይን እማኞች ለዘ-ሐበሻ ገልጸዋል:: እንደ አይን እማኞቹ ገለጻ ህዝቡ በአንድ ላይ ተነጋግሮ ከቤት አለመውጣቱና ከተማዋን ጭር ማድረጉ ስር ዓቱን አስደንግጦታል::

የጎንደር ነዋሪዎች የቤት ውስጥ መቀመጥ አድማው ነገም እንዲቀጥል ጥሪ አቅርቧል::

 


የት ናችሁ የትግራይ ልሂቃን?

$
0
0
file photo

file photo

ከአንተነህ መርዕድ

ነሃሴ 2016

በስማችሁ የተደራጀው ዘረኛና ዘራፊ ቡድን የንፁህ ኢትዮጵያን ልጆች ደም እንደጎርፍ ሲያፈስስ ምነው ድምፃችሁ ጠፋ?

የኦጋዴኖች መጨፍጨፍና ሬሳቸው በሜዳ ላይ መጎተት፣ የጋምቤላዎች በጅምላ መታረድ፣ የኦሮሞዎችና የአማራዎች በጠራራ ፀሃይ በአነጣጥሮ ተኳሽ ትግርኛ ተናጋሪ አጋዚ በየሜዳው መደፋት እንዴት ህሊናችሁን አልኮሰኮሳችሁም?

በጣት የሚቆጠሩ  ዘራፊዎች ነገን አጨልመውባችሁ ሊሄዱ ሲዘጋጁ እንዴት አልታያችሁ አለ?

ባለፉት ሃያ አምስት ዓመታት ህልውናውን እንዲያጣና የግፍ ፅዋ እንዲጨልጥ የተገደደው መላው ኢትዮጵያዊ፤ “ከዚህ በኋላ በቃኝ፣ ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ነፃነቴን ማግኘት አለብኝ” ብሎ መንቀሳቀስ መጀመሩን ዓለም ሲመሰክር እንዴት አልከሰትላችሁ አለ?

እስከአሁኗ ደቂቃ የኢትዮጵያ ህዝብ እባካችሁ በፍቅርና በእኩልነት እንኑር እያለ የሚያሰማው ልመናና ጩኸት ላለማስማት ምን አገዳችሁ?

ይህ ዘራፊና ዘረኛ ቡድን በስልጣን ለመቆየት ከሁሉም በላይ በትግራይ ህዝብ ዘላቂ ህልውና ላይ እንደዘመተበትና የእሱን ሃጢያት እዳ ከፋይ ሆኖ እንዲኖር እንደፈረደበት አይታታችሁም?

ከሚሞት ጥቂት የአምባገነን ቡድን ጋር በማበራችሁና ዝምታን በመምረጣችሁ እንዴት የዋህና ድሃ የትግራይ ህዝብ ሲጎዳ አልታያችሁ አለ? ህወሃት የትግራይን ህዝብ ጥቅም በዘላቂው እንደጎዳ ለመናገር አንደበታችሁን ምን ዘጋው?

አዎ! ከሌላው ኢትዮጵያዊ በተለየ የሥራ መስክ ተከፍቶላችኋል። ሁሉንም የአገሪቱን ሃብት፣ መከላከያውን፣ ደህንነቱን ስልጣኑን ሙሉ በሙሉ በተቆጣጠረው ቡድን ተጠቃሚ ሆናችኋል። ለመማርና ሳትማሩም ለትልልቅ የጥቅም ቦታዎች ያለገደብ ተሳታፊ እንድትሆኑ ተመቻችቶላችኋል። ሌላው ሲገደል፣ ሲታሰር፣ ሲዘረፍና አገሩን ጥሎ ሲሰደድ ሁሉም በር በሞኖፖል ተከፍቶላችኋል። ነገር ግን ምስኪኑ በሚሊዮን የሚቆጠረው የትግራይ ህዝብ በድህነት እያለ ከኢትዮጵያውያን ወንድሞቹ ጋር የሚኖረውን ዘላቂ ጥቅሙን በጊዜያዊ ድሎታችሁ ነግዳችሁበታል።

በአጋዚ አልሞ ተኳሽ ህፃናት ኢትዮጵያውን ሲደፉ፣ ህዝቡ ሃዘን ውስጥ ተቀምጦና ዓለም ያየውን ዘግናኝ ነገር ለማመን እስኪቸገር ሲያዝን ውስኪ እየተራጫችሁ ስትጨፍሩ በምትደልቁት አተሞ ስትደነቁሩ፣ ወይም እንዳላያችሁ ፀጥታን ስትመርጡ፤ እንኳንስ የትግራይን ህዝብ የራሳችሁንም ቀጣይ ጥቅም በሚያስዘነጋ የቅዠት ዓለም ውስጥ መሆናችሁ እየታየ ነው።

በህወሃት የቅዠት ዓለም ውስጥ ሳይሆን እውነተኛዋን ትግራይን ተመልከቱ፡

  • በብዙ ሺህ ኪሎሜትር ከሚዋሰነው፣ ለዘመናት አብሮት ከኖረው፣ ከተዋለደው ከተዛመደው ከወንድሙ ከኤርትራ ህዝብ አቆራርጠውታል።
  • ከላይ ከጎንደር፣ ወሎና አፋር ድረስ በዘረኝነት በተሞላው ስግብግብነትና ትዕቢት ከአማራው፣ ከአገው፣ ከአፋሩ ደም አቃብተውታል።
  • ከሰፊው የኦሮሞ ህዝብ ንብረቱንና የልጆቹን ህይወት በመንጠቅ ለያይተውታል።
  • ጋምቤላዎችን በማጨፋጨፍና በመጨፍጨፍ፣ መሬቱን በመዝረፍና ለውጭ ባለሃብቶች በመሽጥ አስሰድደውታል።
  • ኦጋዴንን ህዝብ በጅምላ ገድለውታል፤ በርሃብ ዓለም እንዳይደርስለት ቀጥተውታል።
  • መሃል አዲስ አበባና ዳር ለዳር የሚኖረውን ድሃ ህዝብ አፈናቅለው ሜዳ ላይ በመጣል እነአቦይ ሰማይ ጠቀስ ፎቅ ገንብተውበታል።
  • በዓለም ዙርያ ያሉ የኢትዮጵያ ኤምባሲዎች የህወሃት የግል ቢሮና የአንድ ዘር ተጠቃሚነትን በግልፅ በማወጅ ቀሪውን ኢትዮጵያዊ አግልለውበታል።

ይህ ሁሉ ግፍና ያልተዘረዘረው ወንጀል ምን ያህል ጊዜ ይዘልቃል ብላችሁ ብታስቡ ነው ማዕበሉን ላለማየት አሸዋ ውስጥ እራሷን እንደቀበረችው ሰጎን በጊዜያው ጥቅም ውስጥ ራሳችሁን ደብቃችሁ በማስገምገም ላይ ያለው ህዝባዊ ማዕበል አልታያችሁ ያለው? ከሁሉም የተነጠለች ትግራይ ዕድሏ ከሱዳን ጋር ብቻ እንዲሆን ወሰናችሁ ማለት ነው? የሚቻል አይደለም።

ከሃያ ዓመት በፊት ጥቂት ትዕቢት በወጠራቸው የሻዕብያ ሰዎች ኢትዮጵያውያንን የመናቅ፣ በሃብት በንብረቷ አዛዥና ናዛዥ መሆናቸው እንዴት እንዳሳወራቸው ትምህርት የሚሆነን ይመስለኛል። የኤርትራ ኤምባሲ እንደማዕከላዊ ይፈራ ነበር።የራሱ እስር ቤትና ማሰቃያ ነበረውና። “አፍሪካዊት ሲንጋፖር” የምትሆነውን ኤርትራን ለመገንባት ያለሙት ግን በኢትዮጵያ ጥሬ ሃብትና ገበያ ላይ ነበር። ቅዠት እውነት አይደለምና ከእንቅልፋቸው ሲባንኑ ወንድሞቻችን ኤርትራውያንም እኛም አሁን ካለንበት እንገኛለን። የዘሩትን ማጨድ ይሏል ይህ ነው።

የመከላከያው ተቋም ተነቃቅሎ ትግራይ ተገንብቷል። ብዙ ትልልቅ ነገሮች ከመሃል አገር እየተነቀሉ ወደትግራይ የመሄዳቸው ጉዳይ “በጠላት” የሚነገር ፕሮፓጋንዳ ሳይሆን የአለፉት ሃያ ዓምስት ዓመታት እውነታ ሲሆን በትናንቱ ዜና ደግሞ የቴሌኮሙኒኬሽን የመረጃ ቋት (ዳታ ሲስተም) ከአዲስ አበባ ተነቅሎ መቀሌ መተከሉ ስንሰማ የህወሃትን የዕብደት መጠን ከመግለፅ ባሻገር እንግዳ ባህሪ አያደርገውም። አፍ የሚችለውን እጅ ይመጥናል ይባላልና ህወሃት ግን መዋጥ የሚችለውን አይደለም እያነሳ ያለው። ይልቅስ የስስታም መጨረሻው በጎረሰው ታንቆ መሞት ነውና እናየዋለን። ለመሆኑ ለይስሙላ የተቀመጡት የፌደራል ባለስልጣናት እነኃይለማርያም  ዋና ከተማቸውንም መቀሌ እስኪሆን ነው የሚጠብቁት?

እዚህ ላይ ህዝቡ በትዝብት የገጠማትን ላካፍላችሁ።

የሚጓጓዝ ቢሆን ሁሉም በመኪና

ትግራይ ውስጥ ነበሩ አባይና ጣና። ብለዋል።

ግድ የለም ፋብሪካውም ይሂድ፣ ሁሉንም የቻሉትን ይውሰዱ። በቅዠት ዓለም ውስጥ የሚያልሟት ትግራይ አየር ላይ ነው የምትገነባው? ጥሬ እቃው፣ የሃይል አቅርቦቱ፣ ገበያው ከየት ነው? በስልጣን ጥም የተመረዙ ህወሃቶች ይህ ሁሉ እንደማይሳካ ቢያውቁትም የትግራይን ህዝብ እንደሰባዊ ጋሻ መያዣነት ለመጠቀም ነው። ለእውነተኛ የትግራይ ዘላቂ ልማት ቢያስቡት ከኢትዮጵያ ህዝብ ተለይቶ ከቶም የትግራይ ህዝብ ሊያድግ አይችልም። ከገፉበትና ድጋፍ ካገኙ ለታሪክ የሚተው ፀፀት የሚያስይዝ ህንፃ ብቻ ሆኖ ነው የሚቀረው። ለመሆኑ የትግራይ ልሂቃን ይህ እንዴት ይጠፋችኋል? ብቸኛ ተጠቃሚነታችሁ ምን ያህል ይዘልቃል ብላችሁ ታስባላችሁ? ለአፈራችሁት ሃብትና ቤተሰብ ዋስትና የሚሰጣችሁ የኢትዮጵያ ህዝብ እንጂ የሚሞት ስርዓት አይደለም።

የስብሃት ነጋ፣ የአባይ ወልዱ፣ የስዩም መስፍን፣ የአባይ ፀሃዬ፣ የአዜብ መስፍን፣ የብርሃነ ገብረክርስቶስ፣ የቴዎድሮስ አድሃኖም፣ ምን አለፋችሁ የትልልቆቹ ህወሃት ባለስልጣናት በቢልዮን የሚቆጠር የዘረፉት ንብረትና ቤተሰባቸው ውጭ ነው ያለው? ለምን ትግራይ ውስጥ ያንን ሃብት አላፈሰሱትም? እንደመንግስቱ ኃይለማርያም የዘረፋና የወንጀሉ ተባባሪ ጓዶቻቸውን ጥለው እብስ ለማለት ዝግጁ ናቸው። ውሃ ሃጅ ደንጋይ ቀሪ እንደሚባለው የስርዓቱ ተባባሪ ሆናችሁ ያስገደላችሁና ያስዘረፋችሁ እንደነለገሰ አስፋው ጎርፉን መጠበቅ ሊኖርባችሁ ነው። የዚች አገር ታሪክ እንደሆነ ራሱን የሚደጋግም ነው። ህወሃቶች ለአፈሰሱት የንፁሃን ደም፣ ለዘረፉት ንብረት፣ ለአደረሱት ሰቆቃ እዳ ከፋዩ እዚያው ይቀራል። የትግራይ ልሂቃንና የትግራይ ህዝብ በፍጥነት ከቀሪው የኢትዮጵያ ህዝብ ጋር ካልቆመ የሚመጣውን ጉዳት ማሰቡ ያስፈራል።

ኦሮሞው፣ አማራው፣ ሶማሌው፣ ደቡቡ፣ ጋምቤላው፣ መሃል አዲስ አበባ፣ በአጠቃላይ ሁሉም ኢትዮጵያዊ ለዘረኛውና ዘራፊው ህወሃት ላለመገዛት መቁረጡና መንቀሳቀሱ ካልተሰማችሁ መልካም እንቅልፍ። የኢትዮጵያ ህዝብ ከዚህ የከፋ ምንም አይደርስብኝም ብሎ ተነስቷል። ኳሷ እጃችሁ ላይ ናት። ውጤቱም እንደምርጫችሁ ይወሰናል። ፈጥናችሁ የትግራይንና የኢትዮጵያ ህዝብ ካንጃበበት መከራ ለመታደግ የትግሉ አካል ሁኑ። ህዝቡ እያለቀሰና እየጮኸ በዝምታችሁ ከቀጠላችሁ እናንተ ስታለቅሱ ሌላው በዝምታ የሚታዘባችሁ ቀን ተቃርቧል። ልቦና ይስጣችሁ።

ኢትዮጵያን የቁርጥ ቀን ልጆቿ ይታደጓታል!

መከራው በትግላችን ያበቃል!

የት ናችሁ የትግራይ ልሂቃን? –ከአንተነህ መርዕድ

$
0
0

ነሃሴ 2016
13934987_153112055123291_7181282795788322844_nበስማችሁ የተደራጀው ዘረኛና ዘራፊ ቡድን የንፁህ ኢትዮጵያን ልጆች ደም እንደጎርፍ ሲያፈስስ ምነው ድምፃችሁ ጠፋ?

የኦጋዴኖች መጨፍጨፍና ሬሳቸው በሜዳ ላይ መጎተት፣ የጋምቤላዎች በጅምላ መታረድ፣ የኦሮሞዎችና የአማራዎች በጠራራ ፀሃይ በአነጣጥሮ ተኳሽ ትግርኛ ተናጋሪ አጋዚ በየሜዳው መደፋት እንዴት ህሊናችሁን አልኮሰኮሳችሁም?

በጣት የሚቆጠሩ  ዘራፊዎች ነገን አጨልመውባችሁ ሊሄዱ ሲዘጋጁ እንዴት አልታያችሁ አለ?

ባለፉት ሃያ አምስት ዓመታት ህልውናውን እንዲያጣና የግፍ ፅዋ እንዲጨልጥ የተገደደው መላው ኢትዮጵያዊ፤ “ከዚህ በኋላ በቃኝ፣ ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ነፃነቴን ማግኘት አለብኝ” ብሎ መንቀሳቀስ መጀመሩን ዓለም ሲመሰክር እንዴት አልከሰትላችሁ አለ?

እስከአሁኗ ደቂቃ የኢትዮጵያ ህዝብ እባካችሁ በፍቅርና በእኩልነት እንኑር እያለ የሚያሰማው ልመናና ጩኸት ላለማስማት ምን አገዳችሁ?

ይህ ዘራፊና ዘረኛ ቡድን በስልጣን ለመቆየት ከሁሉም በላይ በትግራይ ህዝብ ዘላቂ ህልውና ላይ እንደዘመተበትና የእሱን ሃጢያት እዳ ከፋይ ሆኖ እንዲኖር እንደፈረደበት አይታታችሁም?

ከሚሞት ጥቂት የአምባገነን ቡድን ጋር በማበራችሁና ዝምታን በመምረጣችሁ እንዴት የዋህና ድሃ የትግራይ ህዝብ ሲጎዳ አልታያችሁ አለ? ህወሃት የትግራይን ህዝብ ጥቅም በዘላቂው እንደጎዳ ለመናገር አንደበታችሁን ምን ዘጋው?

አዎ! ከሌላው ኢትዮጵያዊ በተለየ የሥራ መስክ ተከፍቶላችኋል። ሁሉንም የአገሪቱን ሃብት፣ መከላከያውን፣ ደህንነቱን ስልጣኑን ሙሉ በሙሉ በተቆጣጠረው ቡድን ተጠቃሚ ሆናችኋል። ለመማርና ሳትማሩም ለትልልቅ የጥቅም ቦታዎች ያለገደብ ተሳታፊ እንድትሆኑ ተመቻችቶላችኋል። ሌላው ሲገደል፣ ሲታሰር፣ ሲዘረፍና አገሩን ጥሎ ሲሰደድ ሁሉም በር በሞኖፖል ተከፍቶላችኋል። ነገር ግን ምስኪኑ በሚሊዮን የሚቆጠረው የትግራይ ህዝብ በድህነት እያለ ከኢትዮጵያውያን ወንድሞቹ ጋር የሚኖረውን ዘላቂ ጥቅሙን በጊዜያዊ ድሎታችሁ ነግዳችሁበታል።

በአጋዚ አልሞ ተኳሽ ህፃናት ኢትዮጵያውን ሲደፉ፣ ህዝቡ ሃዘን ውስጥ ተቀምጦና ዓለም ያየውን ዘግናኝ ነገር ለማመን እስኪቸገር ሲያዝን ውስኪ እየተራጫችሁ ስትጨፍሩ በምትደልቁት አተሞ ስትደነቁሩ፣ ወይም እንዳላያችሁ ፀጥታን ስትመርጡ፤ እንኳንስ የትግራይን ህዝብ የራሳችሁንም ቀጣይ ጥቅም በሚያስዘነጋ የቅዠት ዓለም ውስጥ መሆናችሁ እየታየ ነው።

በህወሃት የቅዠት ዓለም ውስጥ ሳይሆን እውነተኛዋን ትግራይን ተመልከቱ፡

  • በብዙ ሺህ ኪሎሜትር ከሚዋሰነው፣ ለዘመናት አብሮት ከኖረው፣ ከተዋለደው ከተዛመደው ከወንድሙ ከኤርትራ ህዝብ አቆራርጠውታል።
  • ከላይ ከጎንደር፣ ወሎና አፋር ድረስ በዘረኝነት በተሞላው ስግብግብነትና ትዕቢት ከአማራው፣ ከአገው፣ ከአፋሩ ደም አቃብተውታል።
  • ከሰፊው የኦሮሞ ህዝብ ንብረቱንና የልጆቹን ህይወት በመንጠቅ ለያይተውታል።
  • ጋምቤላዎችን በማጨፋጨፍና በመጨፍጨፍ፣ መሬቱን በመዝረፍና ለውጭ ባለሃብቶች በመሽጥ አስሰድደውታል።
  • ኦጋዴንን ህዝብ በጅምላ ገድለውታል፤ በርሃብ ዓለም እንዳይደርስለት ቀጥተውታል።
  • መሃል አዲስ አበባና ዳር ለዳር የሚኖረውን ድሃ ህዝብ አፈናቅለው ሜዳ ላይ በመጣል እነአቦይ ሰማይ ጠቀስ ፎቅ ገንብተውበታል።
  • በዓለም ዙርያ ያሉ የኢትዮጵያ ኤምባሲዎች የህወሃት የግል ቢሮና የአንድ ዘር ተጠቃሚነትን በግልፅ በማወጅ ቀሪውን ኢትዮጵያዊ አግልለውበታል።

ይህ ሁሉ ግፍና ያልተዘረዘረው ወንጀል ምን ያህል ጊዜ ይዘልቃል ብላችሁ ብታስቡ ነው ማዕበሉን ላለማየት አሸዋ ውስጥ እራሷን እንደቀበረችው ሰጎን በጊዜያው ጥቅም ውስጥ ራሳችሁን ደብቃችሁ በማስገምገም ላይ ያለው ህዝባዊ ማዕበል አልታያችሁ ያለው? ከሁሉም የተነጠለች ትግራይ ዕድሏ ከሱዳን ጋር ብቻ እንዲሆን ወሰናችሁ ማለት ነው? የሚቻል አይደለም።

ከሃያ ዓመት በፊት ጥቂት ትዕቢት በወጠራቸው የሻዕብያ ሰዎች ኢትዮጵያውያንን የመናቅ፣ በሃብት በንብረቷ አዛዥና ናዛዥ መሆናቸው እንዴት እንዳሳወራቸው ትምህርት የሚሆነን ይመስለኛል። የኤርትራ ኤምባሲ እንደማዕከላዊ ይፈራ ነበር።የራሱ እስር ቤትና ማሰቃያ ነበረውና። “አፍሪካዊት ሲንጋፖር” የምትሆነውን ኤርትራን ለመገንባት ያለሙት ግን በኢትዮጵያ ጥሬ ሃብትና ገበያ ላይ ነበር። ቅዠት እውነት አይደለምና ከእንቅልፋቸው ሲባንኑ ወንድሞቻችን ኤርትራውያንም እኛም አሁን ካለንበት እንገኛለን። የዘሩትን ማጨድ ይሏል ይህ ነው።

የመከላከያው ተቋም ተነቃቅሎ ትግራይ ተገንብቷል። ብዙ ትልልቅ ነገሮች ከመሃል አገር እየተነቀሉ ወደትግራይ የመሄዳቸው ጉዳይ “በጠላት” የሚነገር ፕሮፓጋንዳ ሳይሆን የአለፉት ሃያ ዓምስት ዓመታት እውነታ ሲሆን በትናንቱ ዜና ደግሞ የቴሌኮሙኒኬሽን የመረጃ ቋት (ዳታ ሲስተም) ከአዲስ አበባ ተነቅሎ መቀሌ መተከሉ ስንሰማ የህወሃትን የዕብደት መጠን ከመግለፅ ባሻገር እንግዳ ባህሪ አያደርገውም። አፍ የሚችለውን እጅ ይመጥናል ይባላልና ህወሃት ግን መዋጥ የሚችለውን አይደለም እያነሳ ያለው። ይልቅስ የስስታም መጨረሻው በጎረሰው ታንቆ መሞት ነውና እናየዋለን። ለመሆኑ ለይስሙላ የተቀመጡት የፌደራል ባለስልጣናት እነኃይለማርያም  ዋና ከተማቸውንም መቀሌ እስኪሆን ነው የሚጠብቁት?

እዚህ ላይ ህዝቡ በትዝብት የገጠማትን ላካፍላችሁ።

የሚጓጓዝ ቢሆን ሁሉም በመኪና

ትግራይ ውስጥ ነበሩ አባይና ጣና። ብለዋል።

ግድ የለም ፋብሪካውም ይሂድ፣ ሁሉንም የቻሉትን ይውሰዱ። በቅዠት ዓለም ውስጥ የሚያልሟት ትግራይ አየር ላይ ነው የምትገነባው? ጥሬ እቃው፣ የሃይል አቅርቦቱ፣ ገበያው ከየት ነው? በስልጣን ጥም የተመረዙ ህወሃቶች ይህ ሁሉ እንደማይሳካ ቢያውቁትም የትግራይን ህዝብ እንደሰባዊ ጋሻ መያዣነት ለመጠቀም ነው። ለእውነተኛ የትግራይ ዘላቂ ልማት ቢያስቡት ከኢትዮጵያ ህዝብ ተለይቶ ከቶም የትግራይ ህዝብ ሊያድግ አይችልም። ከገፉበትና ድጋፍ ካገኙ ለታሪክ የሚተው ፀፀት የሚያስይዝ ህንፃ ብቻ ሆኖ ነው የሚቀረው። ለመሆኑ የትግራይ ልሂቃን ይህ እንዴት ይጠፋችኋል? ብቸኛ ተጠቃሚነታችሁ ምን ያህል ይዘልቃል ብላችሁ ታስባላችሁ? ለአፈራችሁት ሃብትና ቤተሰብ ዋስትና የሚሰጣችሁ የኢትዮጵያ ህዝብ እንጂ የሚሞት ስርዓት አይደለም።

የስብሃት ነጋ፣ የአባይ ወልዱ፣ የስዩም መስፍን፣ የአባይ ፀሃዬ፣ የአዜብ መስፍን፣ የብርሃነ ገብረክርስቶስ፣ የቴዎድሮስ አድሃኖም፣ ምን አለፋችሁ የትልልቆቹ ህወሃት ባለስልጣናት በቢልዮን የሚቆጠር የዘረፉት ንብረትና ቤተሰባቸው ውጭ ነው ያለው? ለምን ትግራይ ውስጥ ያንን ሃብት አላፈሰሱትም? እንደመንግስቱ ኃይለማርያም የዘረፋና የወንጀሉ ተባባሪ ጓዶቻቸውን ጥለው እብስ ለማለት ዝግጁ ናቸው። ውሃ ሃጅ ደንጋይ ቀሪ እንደሚባለው የስርዓቱ ተባባሪ ሆናችሁ ያስገደላችሁና ያስዘረፋችሁ እንደነለገሰ አስፋው ጎርፉን መጠበቅ ሊኖርባችሁ ነው። የዚች አገር ታሪክ እንደሆነ ራሱን የሚደጋግም ነው። ህወሃቶች ለአፈሰሱት የንፁሃን ደም፣ ለዘረፉት ንብረት፣ ለአደረሱት ሰቆቃ እዳ ከፋዩ እዚያው ይቀራል። የትግራይ ልሂቃንና የትግራይ ህዝብ በፍጥነት ከቀሪው የኢትዮጵያ ህዝብ ጋር ካልቆመ የሚመጣውን ጉዳት ማሰቡ ያስፈራል።

ኦሮሞው፣ አማራው፣ ሶማሌው፣ ደቡቡ፣ ጋምቤላው፣ መሃል አዲስ አበባ፣ በአጠቃላይ ሁሉም ኢትዮጵያዊ ለዘረኛውና ዘራፊው ህወሃት ላለመገዛት መቁረጡና መንቀሳቀሱ ካልተሰማችሁ መልካም እንቅልፍ። የኢትዮጵያ ህዝብ ከዚህ የከፋ ምንም አይደርስብኝም ብሎ ተነስቷል። ኳሷ እጃችሁ ላይ ናት። ውጤቱም እንደምርጫችሁ ይወሰናል። ፈጥናችሁ የትግራይንና የኢትዮጵያ ህዝብ ካንጃበበት መከራ ለመታደግ የትግሉ አካል ሁኑ። ህዝቡ እያለቀሰና እየጮኸ በዝምታችሁ ከቀጠላችሁ እናንተ ስታለቅሱ ሌላው በዝምታ የሚታዘባችሁ ቀን ተቃርቧል። ልቦና ይስጣችሁ።

ኢትዮጵያን የቁርጥ ቀን ልጆቿ ይታደጓታል!

መከራው በትግላችን ያበቃል!

 

 

ህወሓት/ኢህአዴግ ከስልጣን ይውረድ! የሽግግር መንግስት ይቋቋም [ከትግራይ ተወላጆች የተሰጠ መግለጫ]

$
0
0

8 ነሓሴ 2008

tplf-rotten-apple-1.jpgበአጠቃላይ ለ25 ዓመታት ሙሉ ህዝባችንን አፍኖ ሲገዛ የቆየና፣ ለ40 ዓመታት ሰላማዊ ዜጎችን እየረሸኑ አገራችንን እየዘረፉ የቆዩ ባለስልጣኖች ያሉበት ህወሓት/አህአዴግ በተለይ በዚህ ዓመት በኦሮሞና በአማራ ህዝባችን ላይ ጦርነት ከፍቷል። የአገዛዙን የግድያ ወንጀሎች እናወግዛለን፤ የህዝቡን ተቃውሞ እንደግፋለን።

ስለዚህ በአገራችን ዴሞክራሲያዊ ስርዓት እንዲገነባ፣ የህዝባችን አንድነት እንዲጠናከርና የአገራችን ሉኣላዊነት እንዲከበር᎓

[ሙሉውን ለማንበብ እዚህ ይጫኑ]

በባህርዳር በተከሰተ ኮሌራ ከ30 በላይ ሰዎች ታመሙ | 15 ሰዎች ሞተዋል

$
0
0
(የባህር ዳር ከተማ)

(የባህር ዳር ከተማ)

(ዘ-ሐበሻ) ባህርዳር በተለምዶው አንዳሳ በሚባለው አካባቢ በተከሰተ ኮሌራ በርካታ ሰዎች መታመማቸው ተሰማ:: 15 ሰዎች ሕይወታቸው ማለፉም ምንጮች ተናግረዋል::

በባህርዳር አዲስ ዓለም ሆስፒታል ውስጥ የታመሙት ከ30 በላይ ሰዎች እየታከሙ መሆኑ ሲሰማ 15 ሰዎች ሕይወታቸው ማለፉ ታውቋል::

በባህርዳር ሕዝባዊ ተቃውሞ እየተደረገ ባለበት በዚህ ወቅት እስካሁን ያልተከሰተው ኮሌራ አሁን ተከሰተ መባሉ ብዙዎችን እያነጋገረ ባለበት በዚህ ሰዓት ምናልባት ስርዓቱ በአማራው ሕዝብ እየደረሰበት ያለውን ተቃውሞ አቅጣጫ ለማስቀየር ሆን ብሎ ያደረገው ሊሆን ይችላል የሚሉ አስተያየት ሰጪዎች አሉ::

በተለይ ይህ ኮሌራ በአንድ አካባቢ ብቻ ማለትም አንዳሳ በተባለው ቦታ ብቻ ተከሰተ መባሉ አነጋጋሪ ሲሆን ሆን ተብሎ ውሃን በመበከል የተደረገ እንዳይሆን የሚሉ ጥርጣሬዎች አለ:: በዚህም መሰረት ማንኛውም የባህርዳር ነዋሪ ውሃን አፍልቶ እንዲጠጣ ጥሪ ቀርቧል::

በተለይ በዚህ ሰሞን በሶሻል ሚድያዎች ስርዓቱ የትግራይ ተወላጆችን ከጎንደር እና ባህርዳር እያስወጣ ባለበት ወቅት አማራውን ለመመረዝ ሴራ እየተጎነጎነ ነው የሚሉ ወሬዎች ሲሰራጩ ነበር::

የጎንደር ከንቲባና የሰሜን ጎንደር የፀጥታ ዘርፍ ኃላፊ በትግራይ ነፃ አውጪ ግምባር ከስልጣናቸው ተነሱ

$
0
0

Zehabesha-News.jpg

ከቤተ አማራ – Bete Amhara

የጎንደር ከተማ ከንቲባ አቶ ተቀባ ተባበል እና የሰሜን ጎንደር የፀጥታ ዘርፍ ሃላፊው አቶ ዋኝው ዋዋ ከስልጣናቸው በሕወሓት ሰዎች አማካኝነት እንደተነሱ መረጃ ደርሶናል።

ምንጫችን እንደገለፁት ሁለቱ ባለስልጣናት በኮሎኔል ደመቀ ዘውዱ ጉዳይ ለዘብተኛ አቋም በመያዛቸው ህወሓቶችን ጥርስ ውስጥ ገብተው ሰንብተዋል። በዚህም ምክንያት በስልት ለሌላ ስራ እንደታጩ በማስመሰል ከስልጣናቸው እንዲወርዱ ተደርጓል ። በምትካቸው ፀረ አማራ አቋም ያላቸው የህወሓት ስራ አስፈፃሚዎች ውስጥ ለውስጥ እንደተሾሙም ምንጫችን አያይዘው ገልፀዋል። በመሆኑም የኮሎኔል ደመቀ ዘውዱ ጉዳይ አሳሳቢ ደረጃ ላይ ይገኛል።

በማንኛውም ሰአት ከጎንደር አፍነው ሊወስዱት ይችላሉ ተብሎ ይጠበቃል። የአርማጭሆ የጠገዴ እና የወልቃይት ገበሬዎች ከጎንደር ህዝብ ጋር ሆነው ሃምሌ 6 ቀን 2008 ዓም ኮለኔል ደመቀ ዘውዱን ለአቶ ተቀባ እና ለአቶ ዋኘው በአደራ መስጠታቸው ይታወሳል ።

ሌንጮ ባቲ እና ነአምን ዘለቀ በኦሮሞ ዴሞክራሲያዊ ግምባር እና በአርበኞች ግንቦት 7 ንቅናቄ ጥምረት ዙሪያ ለሕብር ራድዮ ቃለምልልስ ሰጡ |ይዘነዋል

$
0
0

(ዘ-ሐበሻ) የኦሮሞ ዴሞክራሲያዊ ግምባር እና አርበኞች ግንቦት 7 በጋራ ለመታገል መወሰናቸውንና ይህንንም ድርጅቶቹ መሪዎች ፊርማ ማረጋገጣቸውን ዘ-ሐበሻ በሰበር ዜና መዘገቧ አይዘነጋም:: የሁለቱ ድርጅቶች አመራሮች አቶ ሌንጮ ባቲ እና አቶ ነአምን ዘለቀ ለሕብር ራድዮ ልዩ ቃለምልልስ ሰጥተዋል:: የሕብር ራድዮ ዋና አዘጋጅ ጋዜጠኛ ሃብታሙ የተለያዩ ጥያቄዎችን አቅርቦ አወያይቷቸዋል:: በዚህ ቃለምልልስ ላይ ከሁለቱ ድርጅቶች ጥምረት በተጨማሪ የአማራ እና የኦሮሞ ማህበረሰብ መቀራረብ ያበሳጫቸው የመንግስት ቃል አቀባዩ አቶ ጌታቸው ረዳ “እሳት እና ጭድ” በሚል በሚያሳፍር ሁኔታ ስለሰጡት አስተያየትም ምላሽ ሰጥተዋል:: ቢያደምጡት አይቆጩበትም::

ሕወሓቶች ስለብአዴን የጻፉት: የብአዴን በበሰበሱ ነፍጠኞች እጅ ተጠልፎ የመውደቁ ትርኢት ወጣ ወጣና ተንከባለለ እንደሙቀጫ

$
0
0

አይጋ ፎረም የተባለው የዘረኛው ሕወሓት መንስት ደጋፊ ድረገጽ ሰሞኑን በብአዴን ላይ ዘምቶበታል:: ” የብአዴን በበሰበሱ ነፍጠኞች እጅ ተጠልፎ የመውደቁ ትርኢት ወጣ ወጣና ተንከባለለ እንደሙቀጫ” የሚል ጽሁፍም በ እንግሊዘኛ ቋንቋ አስነብቦ ነበር:: ይህ ጽሁፍ ወደ አማርኛ ተተርጎሞ የቀረበላችሁ ምን ያህል ዘረኞቹ ሕወሓቶች በብ አዴን ላይ ያላቸውን ንቀት እንድታዩት ነው:: ያንብቡት::

በዶር ታረቀኝ በእግሊዝኛ ተጽፎ የቀረበ
መቀሌ
(ዝርግ ትርጉም መስቀሉ አየለ)

የቀደሙት ነገስታት ሆነ ብለው ድርቅን የሚፈጥሩት ብሎም የሚያባብሱት ለማመን በሚቸግር ሁኔታ ህዝቡን ለመቆጣጠር እንዲያስችላቸው ነበር። ነገር ግን ህልቁ መሳፍርት መስዋእትነት ከፍሎ እነዚህን ገዥዎች ከስራቸው ነቅሎ በመጣሉ በኩል የአንበሳውን ድርሻ የተወጣው ጀግናው ህወሃት የማህበራዊና ኢኮኖሚ እቅድ በመንደፍ ባለፈው አመት በኤሊኖ የአየር ጠባይ የተነሳ በአለም አቀፍ ደረጃ ተከስቶ የነበረውን ድርቅ በመቀልበስ ረገድ አመርቂ ውጤት አስመዘገበ። የተመዘገበውም ድል ህወሃትንና አጋሮቹን ያኮራና በአለም አቀፍ ደረጃ ክብርና ሞገስ ጭምር ያስገኘ አኩሪ ታሪክ ሆኖ አልፎዋል። ህወሃት ሁልጊዜም ከምንም ነገር ተነስቶ ተዓምር መፍጠር የዘወትር መለያው ነው።
ANDM

ህወሃት ማለት በመርህ ላይ የቆመ፣ ትጉ፣የማይናወጽ፣ መልካምነት የባህሪ መገለጫው የሆነ፣ ትርፋማ እና በሁሉም ዘርፍ አለማችን እራሷ ከዚህ በፊት አይታው የማታውቀው ተዓምረኛ የፖለቲካ ፓርቲ ነው።በዚህ በጣም ተለዋዋጭ በሆነ አለማቀፋዊ ሁኔታም ውስጥ እንኳን አንድን በጣም ውስብስብ እና ግዙፍ አገርን ስር ከሰደደ ድህነትና ከለየለት ኋላ ቀርነት በማውጣት እንደ አለት የጸና የማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እድገት በማሥመዝገብ በኩል በዓለም ውስጥ ብቸኛው የፖለቲካ ፓርቲ ለመሆን በቅቷል::

ያለመታደል ሆኖ ባለፈው አመት ተከስቶ የነበርውን የድርቅ አደጋ አመርቂ በሆነ ሁኔታ ተቋቁመነው እንዳበቃን ብዙም ሳይቆይ በብዙ የአገሪቱ ክፍሎች ህዝባዊ ነውጥ ተነሳ ።የዚህም ህዝባዊ ነውጥ ዋነኛ ምክንያቱ የኪራይ ሰብሳቢነት ያስከተለው ችግር ቢሆንም ነገር ግን በአማራ ክልል የተነሳውን አመጽ በተመለከተ ግን መሰረታዊ ምክንያቱ ከዚህም አልፎ የሄደ ነበር ማለት ይቻላል ።ይኽውም ህወሃት ብዙ የደከመለትን የአገሪቱን የፖለቲካ መዋቅር ቀስ በቀስ በመገዳደርና ብአዴንን ከቆመለት ህዝባዊነት በማውረድ ግዜው ያለፈበትንና የቆሸሸውን የድሮ ነፍጠኛ ስርዓት ቅርጽ መስጠትን አላማ ያደርገ አፈንጋጭ የብአዴን ክንፍ ከፍተኛው የስልጣን እርከን ላይ መፈናጠጡ ነበር። ብአዴን እንደ አንድ ድርጅት መበስበሱንና ሙሉ በሙሉ በሚባል ደረጃ በእንደዚህ አይነት የነፍጠኛ እርዝራዦች ቁጥጥር ስር መውደቁን የሚያሳዩ የተወሰኑ ትዕይንቶችን ደረጃ በደረጃ ላሳይ።

ትዕይንት ፩

ብአዴን የሰላሳ አምስተኛ አመት የምስረታ በዓሉን ባከበረበት ግዜ ለራሱ ያልነበረ ቅርጽ በመስጠትና ደርግን በመጣሉ ሂደት ውስጥ ወሳኝ ሚና የተጫወተ በማስመሰል የታሪክ ውርጃ በመፈጸሙ የተነሳ በወቅቱ ሁኔታው ያሳሰባቸው ብዙ ሰዎች ድምጻቸውን ለማሰማት ሞክረዋል። ብአዴን የራሱ ነፍስ የሌለው ደርግን ለመጣልም በተደረገው ትግልም ብአዴኖቹ ከሞነጫጨሯቸው ጥቂት ግጥሞችና የፍቅር ደብዳቤዎች ውጭ ምንም ሚና የተጫወቱት ነገር አለመኖሩም ገሃድ የወጣ እውነት ነው።እንደውም ብአዴን የህወሃትን ገድል የሚያሳይ ቪዲዮ ሰርቆ ፫፭ኛ ዓመት በዓሉን ሲያከብር በአማራ ቴሌቪዥን ላይ ምንም አይነት ለውጥ ሳያደርግ የራሱ ገድል አስመስሎ አሳይቷል። ብአዴን ይህንን ያደረገው በጦርነቱ ወቅት በባልተቤትነት ይዞት የነበረ አንድ ነጠላ የቪዲዮ ክር እንኳን ስለመኖሩ የሚታውቅ ነገር በሌለበት ሁኔታ ውስጥ ነው።

በዚሁ የሰላሳ አምስተኛ አመቱ ክብረ በዓል ላይ ከሃቁ ባፈነገጠ መልኩ ተጣመውና ተጋነው ከቀረቡትጭብጦች መካከል ብአዴን ያለማንም እርዳታ በራሱ ግዜ እራሱን ችሎ የተፈጠረ አስመስሎ ለመዘከር የሄደበት ደረጃ ነው። ይህ ማለት ባጭሩ ብአዴንን ህወሃት የፈጠረው አይደለም ለማለት ተፈልጎ ነው። በርግጥ ብአዴን የህወሃት ስራ ነው ወይም አይደለም የሚለው ጥያቄ ቁምነገር ሆኖ አይደለም። በጣም አስፈላጊው ነገር ብአዴን ትግራይ ውስጥ በህወሃት የተሰራውን ፕሮጀክት እንዳለ ግልብጦ በመውሰድ የአማራውን ህዝብ ከነበረበት ድህነት በማውጣት ወደ ከፍተኛ የሶሺዮ ኢኮኖሚ እምርታ ማሸጋገሩ ነው። ነገር ግን ብአዴን ከጽንሰቱ ጀምሮ እራሱን ሆኖ የወጣ ለመምሰል የሚሞክርበት ዋናው አለማ በራሱ በብአዴንም ውስጥ ሆነ ከብአዴን ውጭ ያሉትን የነፍጠኛ ቅሪቶችን ሞራል በማጎልበት በውስጣቸው የተፈጠርውን ባዶነት በመሙላት ብሎም ሞራላቸውን ከፍ ለማድረግ ታስቦ የተደረገ መሆኑ እሙን ነው። ስለሆነም የሰላሳ አምስተኛ አመቱን በዓል አከባበር ልብ ላለው ሰው ብአዴን ያው በድሮው ነፍጠኛ መዳፍ ስር እየገባ ለመሆኑ የመጀመሪያው አመላካች ሁኔታ ነበር ማለት ይቻላል።

ትዕይንት ፪
ብአዴን ከህወሃት እንጀራ ልጅነት እንደ ወረደ ጥቂት ሳምንታት ውስጥ በቀጥታ ወደ አንድ አይነኬ ጎሬላ ተዋጊ ቡድንነት ነበር የተቀየረው። ይኽ በነፍጠኛው ተጽእኖ ስር የውደቀው የጎሬላ ሃይል አንድ ብሎ ጠንካራ ክንዱን ማሳረፍ እና መጨፍጨፍ የጀመረው ምንም አይነት መከላከያ ያልነበራቸውን የቅማንት ብሔረሰብ ህጻናትና ሴቶችን ነበር። በምስኪን ቅማንቶች ላይ የተፈጸመው የጅምላ ግድያ በአይነቱም ሆነ በይዘቱ የቀድሞዎቹ ነፍጠኞች በቀሩት የኢትዮጵያ ህዝቦች ላይ ሲፈጽሙት ከኖሩት ጭፍጨፋ ምንም አይነት ልዩነት ያልነበረው ሲሆን ይኽም እንግዲህ የነፍጠኛው ሃይል በግልጽ ስጋ ለብሶ እየመጣ እንደ ነበር የታየበት ሲሆን በቀጣይነት ለመውሰድ ለሚያስበው ግዙፍ ወረራ እንደ ሙከራ የተወደ ነበር ማለት ይቻላል።

ANDM

ትዕይንት ፫
ተወስደዋል የሚባሉት የአማራ መሬቶች በብአዴን ውስጥ አቆቁጠው በወጡት የድል አጥቢያ አርበኞች ሲቀነቀን የቆየ ነው። ይህ ቡድን የመጀመሪያ ጡንቻውን በቅማንቶች ላይ ሲያሳርፍ ከራሳቸው ከቅማንቶችም ሆነ ከማእከላዊ መንግስቱ ይኽ ነው የሚባል ተግዳሮት ያላጋጠመው በመሆኑ ይበልጥ ሃይሉን በማጠናከርና የወሰን ክልሉን ወደ ረባዳማው ምእራብ ትግራይ ወልቃይት በማስፋት ውጥኑን ዳር ለማድረስ ይረዳው ዘንድ ከኢትዮጵያ ጠላቶች ጋር በእጅ አዙር በመመሳጠር ወረራውን በስፋት መያያዝ የጀመረ ሲሆን ይኽም ብአዴን ሙሉ ለሙሉ በነፍጠኛው ቁጥጥር ስር የወደቀ ለመሆኑ ዋነኛው ማረጋገጫ ሆነ።

ሀ) ህዝባዊነትን ያላማከለ የመሬት ወረራ ማካሄድ የኖረ የነፍጠኞች መሰረታዊ መገለጫ ነው
ለ)የወልቃይት ይገባኛል ጥያቄውን ለመግፋት እየተሄደበት ያለውን መንገድ ለሚያየው ታዛቢ የፈደራል መንግስቱን ህገመንግስት ባፍጢሙ የደፋ ነበር ማለት ይቻላል።
ላንድ ብቸኛ ፓርቲ ጥቅም ሲባል የሁሉም ብሄር ብሄረሰቦች ዋስትና የሆነውን ህገመንግስት ጨፍልቆ ማለፍ ሌላው የነፍጠኛ መገለጫ መሆኑ እየታወቀ ብአዴን እንደሚታየው ሙሉ ለሙሉ በሚባል ደረጃ በነፍጠኛው ቁጥጥር ስር ባይወድቅ እንዲህ ያለውን የህገመንግስት ጥሰት ነገሩን በዝምታ ያልፈዋል ብሎ ማሰብ አይቻልም ነበር።

ትዕይንት ፬
በጎንደር የተፈጠረውን አለመርጋጋት በተመለከት ብአዴን የያዘው አቁዋም የሚገርም ሲሆን ይኽ ውም ድርጅቱን ከፊቷ ከተንጣለለው አረንጉዋዴ ሁዳድ በስተቀር ሌላ ነገር የማታይን የሜዳ አህያ አስመስሎታል።ይህ ቡድን ማንኛውንም አይነት ነገር በመጠቀም የትግራይን ህዝብ ከማንገላታት ጀምሮ ህወሃትን በማሸንፍ ኢህአዴግን ማፍረስና የተነጠቀውን ክብሩን ማስመለስ እንደሚችል ያምናል። ለነፍጠኛው ክብር ማለት በሚሊዮን ይሚቆጠሩ ዜጎችን በረሃብ ቸነፈር እየቀጡ ጥቂቶችን ቁንጣን እስኪይዛቸው ከርሳቸውን መሙላትታና ብዙ እዳሪ እንዲወጣቸው ማስቻል ነው። የኦሮሞያ ክልላዊ መንግስት መግለጫ እንዳስቀመጠው “ነፍጠኛ ሲባል ስለ ቡና ሲያስብ ብቻ ጅማን ሰንጋ ሲያስብ ደግሞ ሃረርን የውይይት አርእስት የሚያደርግ ማለት ነው”። ነፍጠኛው በግልጽ ተደራጅቶ ድፍን ጎንደርን የጦርነት ቀጠና ሲያደርጋት፣ የትግራይ ሰዎችን እየመረጠ ሲገድልና በጠራራ ጸሃይ ንብረታቸውን ሲያወድም ብአዴን ተብየው ግን አይኔን ግንባር ያድርገው በማለት ነበር ለዚህ ሃይል የፖለቲካ ሽፋን ሊሰጠው የሞከረው።ይኽን ያህል የውንብድና ተግባር ሲፈጸምና ክልሉን ዳግም ወደ መላኩ ተፈራ የሽብር ዘመን ሲመልሰው ብአዴን ምንም አይነት እርምጃ አለመውሰዱ እንዲሁም የማእከላዊ መንግስትን ድጋፍ አለመጠየቁ የአማራ ብሄራዊ ክልል መንግስትን አቁዋም ጥያቄ ውስጥ የሚያስገባው ይሆናል። በ፩፱፱፯ ዓም በአዲስ አበባ የተዘመረውን (ትግሬ ወደ መቀሌ፣ እቃ ወደ ቀበሌ፣ ወያኔም ወደ ከርቸሌ) የሚለው መዝሙር በጎንደር ዳግም ሲዘመር፣ ንብረትም ሲወድም ሆነ የሰው ህይወት ሲጠፋ ብአዴንም ሆነ አመራሩ ይቅርታ ለመጠየቅ ፈቃደኛ ሳይሆኑ ቀርተዋል።

ትዕይንት ፭
የፌደራል መንግስቱ ልኡካን ተዎካዮች ሳይቀሩ ለስራ ጉብኝት በሚሄዱባቸው አገሮች በሙሉ በአፍቃሬ ደርግና አፍቃሬ ነፍጠኛው ርዝራዥ ቁምስቅላቸውን ያያሉ። ከነዚህ ውስጡ ድምጻቸው ጎልቶ የሚሰማው የአፈረሱ ቀሳውስት፣ የቀይ ሽብር ተዋናዮች እና ወታደሮች እንዲሁም ስም አልባ አዝማሪዎች ሁሉም ከአማራው ብሔር የሚመዘዙ የደርግና የነፍጠኛ ጥርቅም ናቸው። ነገር ግን በተጻጻሪ መልኩ በብአዴን ስም የተቀመጡቱ ነፍጠኞች ክልላቸውን ወክለው ወደ ውጭ አገር በሚሄዱበት ግዜ የሞቀና የደመቀ አቀባበል የሚደረግላቸው መሆኑን የዚያን ሰሞን የዩናትድ ስቴትሱ ጉብኝት ጥሩ ጠቋሚ ነበር። ሰሞኑን በባህርዳር ውስጥ በብአዴን አመራርና የዲያስፖራው ማህበረሰብ መካከል የነበረው ዝግ ስብሰባ ያሳየው ነገር ቢኖር ብአዴን ምን ያህል የነፍጠኛው ሃይል ጀልባ እየሆነ የመጣ መሆኑን ጠቋሚ ነበር። የቀደሙት የብአዴን አመራሮች የህወሃት አሻንጉሊቶች ናቸው እየተባለ ስማቸው ይጠፋ ስለነበር ለስራ ወደ ውጭ አገር ሲሄዱም ከሌላው የፌደራል መንግስት ተወካይ ያነሰ መዋከብ ደርሶባቸው የማያውቅ ሲሆን ባልተለምደ መልኩ በ አሁኑ ሰዓት ያሉት የብአዴን ሰዎች ግን ምን ያህል የክብር አቀባበል እንደሚደረግላቸው ስናይ መሬቱን መልሰው መቀራመት ለሚፈልጉት የአሁን ዘመን ጉልት ናፋቂዎች እና እነሱ ለሚያራምዱት ጭፍን ብሄራዊ ስሜት የተንበረከኩ ለመሆኑ ትልቁ ማሳያ ነው።

ከዚህም በላይ ተጨማሪ ማረጋገጫዎች ሊቆጠሩ የሚችሉ ሲሆን በዋናነት ግን ምን መደረገት ይኖርበታል በአሁኑ ሰዓት የጎንደሩ ነውጥ እያደገና የአመጹ መሪዎችም ሁኔታውን በማጠናከር ወደቀሩት የአማራ አካባቢዎች ለማስፋፋት እየሞከሩ ነው። ችግሩ ይበልጥ አድጎና ገዝፎ በከፍተኛ ፍጥነት እያደገ ከሚሄድበት ኩነት አንጻር ብአዴንም ሆነ የአማራብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ከዚህ በኋላ እንደገና ሊቆጣጠሩት ይችላሉ ተብሎ የማይታሰብ ሲሆን የክልሉ መንግስትም ሆነ ፓርቲው ብ አዴን በሰላሳ ስድስት አመት ታሪኩ የዚህን አንድ መቶኛ ያህል ችግር አጋጥሞት ያውቃል ብሎ ማሰብ አይቻልም።በቅርቡ እንደምናስታውሰው የብአዴን አፈንጋጭ ሹመኞችና የድል አጥቢያ አርበኞች በምርጫ ዘጠና ሰባት ወቅት ባህርዳር ላይ በመሸነፋቸው እና ወንበር በማጣታቸው አደ አዲስ አበባ በመምጣት በፌደራል መንግስቱ ውስጥ የሚንስትርነት ወንበር አገኙ።

በዚህም የተነሳ አፈንጋጮቹ የብአዴን ክፍል በማእከላዊ መንግስት ውስጥ ለረጅም ግዜ ሲመኙት የኖሩትን የህወሃት ወንበር መቆናጠጥ አስቻላቸው። በርግጥ ህልማቸው በራሱ ችግር ነው ማለት አይደለም። ይልቁንም ህወሃት በኢህአዴግ ውስጥ ያለውን ድርሻ በማቻቻል አጋር ድርጅቶቹም የተሻለ ሃላፊነት ይዘው ጠንክረው እንዲወጡና በአገሪቱ ማህበራዊና ኢኮኖሞያዊ እድገት ላይ ገንቢ ሚና እንዲጫወቱ ማስቻል በመርህ ደረጃ ተቀብሎ ሲሰራበት የኖረው ነገር ነበረና። ነገር ግን ውስጥ ውስጡን ሲብላላ ቆይቶ አሁን ችግር ሆኖ የወጣው ይኽ አፈንጋጭ ቡድን መሰረታዊ ከሆነው መርህ ውጭ ባፈነገጠ መልኩ ቀስ በቀስ የማእከላዊውን መንግስት ስልጣን በመቆጣጠርና፣ ህወሃትን በማዳከም ብሎም ከነፍጠኛው ጋር ግንባር በመፍጠር ወደ ለየለት የመሬት ቅርምት ውስጥ በመግባት ላይ መሆኑ ነው። ይህም አፈንጋጭ የብአዴን ክንፍ የነፍጠኛው ቡድን “ሀ “ብሎ ጎንደር በሚገኘው የስታር ሆተል ላይ ጥቃት ሲሰነዝር ሽፋን በመሰጠት ለትግራይ ህዝብ ማስተላለፍ የተፈለገው ማእከላዊ ነጥብ የጥቃቱ ሰለባዎችን ሊታደጋቸው የሚችል አቅም ያለው ህወሃት እንደሌለ ማሳየት የነበረ ሲሆን ነፍጠኛው በሙሉ በዚህ ሰዓት ይህንን ነገር እንደ ትግል እስትራተጅ ይዞት የተነሳው መሆኑን እሙን ነው።

ANDM 2

ብአዴን የህወሃትና የትግራይ ህዝብ ለሰላም ወዳዱ፣ ትሁቱና ወንድሙ ለሆነው የአማራ ህዝብ የተበረከተ ስጦታ ሲሆን አለማውም ይህንን ህዝብ ከነበረበት ስር የሰደደ ድህነትና ኋላ ቀርነት ይዞት ይወጣል በሚል እሳቤ ነበር።ማንም በዚህ ሰዓት በበሰሜን ሸዋ፣ ወሎና ጎንደር በአካል ሄዶ መታዘብ እንደሚችለው ህወሃትና የትግራይ ህዝብ ለእነዚህ አካባቢዎች ከተክህራረዋ ጀምሮ እስከ አሁኗ ሰዓት ድረስ ከማንኛም አይነት አደጋ ዋስትና ከመስጠት ጀምሮ የራሳቸውን ሰዎች ቀርጸው እንዲያወጡና ብሎም ብአዴን የተሻለና ጠካራ አመራር ሆኖ እንዲወጣ ጉልህ ድረሻ ማበርከቱ በራሱ የሚያሳየው ነገር ቢኖር የትግራይ ህዝብና መንግስት ወንድሙ ለሆነው የአማራ ህዝብ ያለውን ፍቅርና አክብሮት እንዳለው አንዱ ማሳያ ነው።

ዛሬ አፍቃሬ ደርግና የነፍጠኛው እርዝራዥ ይኼን ገና ሳይወለድ የጨነገፈ የነፍጠኛውን ስርዓት መልሰው ለማቆም እያለሙ ነው።ነገር ግን አሁን ባለው ተጨባጭ የኢትዮጵያ ፖለቲካ ውስጥ እንዲህ አይነቱ የጨነገፈ ስርዓት ተመልሶ የሚመጣበት ሁኔታ ይፈጠራል ብሎ ማመን ከንቱ ድካም ነው። አፈንጋጩ ብአዴንና እስከ ጥርሳቸው የታጠቁት በአስር ሽህዎች የሚቆጠሩ ምንም የማያውቁት የአማራ ሚሊሽያዎች እንኩዋን ህወሃትን ያህል ሃይል አሰወግደው የነፍጠኛውን ስርዓት ሊያቆሙ ቀርቶ በአንድ የህወሃት ታጋይ የተተከለችውን የማእዘን ድንጋይ ከቦታዋ ማነቃነቅ አይቻላቸውም። ምናልባት ህወሃትን እንደ አንድ ሽፋሽፍት አራክሰውና አሳንሰው ማየት የሚፈልጉ ምንም ግንዛቤ የሌለላቸው አማራዎች ካሉ ልብ እንዲሉት የምንፈልገው ነገር ምንም አይነት መከላከያ የሌላቸውን ህጻናትና ሴቶች በመግደልና በማዋከብ እንዲሆም ንብረታቸውን በመዝረፍ እና ባማቃጠል የነፍጠኛውን ስርዓት መልሰን እናቆምለን ብላችሁ የምታምኑ ከሆነ በሞት የተለየችውን እናቱን ውሃ ልትቀዳ ሄዳ ነው ብሎ ማዶ ማዶ ሲመለከት የሚውልን ህጻን መሆናችሁ እንደሆነ እወቁት።

በማጠቃለል መልካም የሆነውና የተማረው የአማራ ህዝብ ክፍል የነፍጠኛውን ስርዓት እንደገና መልሶ ማቆም ወይንም የሂደቱ አካል አድርጎ ማስቀጠል ይቻላል ብለው ያምናሉ ተብሎ አይገመትም። በምሆኑም ግዜው ከመርፈዱ በፊት ብአዴን “አንድ ” ብሎ ሲነሳ ይዞለት የተነሳውን አላማ እዳይስት የማድረግ ሙሉ ሃላፊነት አለባቸው። ስለዚህ በሌለ እውነት ላይ የተገነባውን እና እንደ ባዶ ፊኛ የተወጠረውን የነፍጠኛ ስሜት በስቸኳይ ማስወገዱ ለነገ የማይባል ጉዳይ ሲሆን የኢህአዴግም ጥምሮች እንደ ፓርቲ ብአዴንን ከተጣባው የነፍጠኛ ጥርቅም እራሱን ያጸዳ ዘንድ የሚቻላቸውን ያህል የመርዳት ሃላፊነት ያለባቸው ሲሆን በመቀጠለም ግዜው ኢህአዴግም እራሱ በውስጡ ከተሰከሰኩ ጠባብ ብሔርተኞች እና ትምክህተኞች ውስጡን የሚያጸዳበት የስር ነቀል ተሃድሶ ግዜ ሊሆን ይገባዋል። ሙስናንም ሆነ ኪራይ ሰብሳቢነትን ውጤታማ በሆነ መልኩ መዋጋት ማለት ይኼው ነው።


ኢትዮጵያውያን በስዊድን ስቶክሆልም ደማቅ ሰላማዊ ሰልፍ አደረጉ |ቪዲዮና ዘገባ

$
0
0


ተሰማ ደሳለኝ | ለዘ-ሐበሻ ከስዊድን
በአሁኑ ሰዓት በሀገራችን የአማራው ህዝብ እያደረገ ያለውን ከፍተኛ መስዋዕትነት ለመደገፍ ና ለማበረታታት እንዲሁም ዘረኛው ወያኔ በወገኖቻችን ላይ እያደረሰ ያለውን ስቃይ ፣እንግልትና ግድያ በመቃወም ሞረሽ ወገኔ በስዊዲን ስቶክሆልም ከተማ ኦገስት 12 ታላቅ ስላማዊ ሰልፍ አካሂዷል ፡፡

በዕለቱም የሞረሽ ወገኔ የስዊዲን ቅርንጫፍ ሊቀመንበር የሆኑት ወ/ሮ ዘውዲቱ የማነ ባደረጉት የመክፈቻ ንግግር ላይ እንደገለፁት ከሆነ ‹‹ ይህ ሰላማዊ ሠልፍ እንዲዘጋጅ ዋንኛ ምክንያት የሆነው የወልቃይት ጠገዴ አማራ በትወልድ ቀዬውና ማንነቱን ፣ ነፃነቱንና ሀገሩን በዘረኛው የወያኔ ትግሬ ቡድን በማናለብኝነት ተነጥቆ ፈላጭ ቆራጩ የትግሬ ነጻ አውጪው ድርጅት የወልቃይት ህዝብ አማርኛ እንዳይናገር ፣እንዳይፅፍ፣ እንዳይዘፍን በመከልከል በሠላም የማንነት ጥያቄ ያቀረቡት አማሮችን እያሰረ ፤ እያፈነና እየገደለ መውጫመግቢያ ስላሳጣው አማራው እንደ አባቶቹ እምቢ ለማንነቴ ፤እምቢ ለነጻነቴና ለክብሬ ብሎ ከጠላቱ ወያኔ ጋር ለሚፋለመው የአማራው ህዝብ አጋር መሆናችንን ለመግለፅና በሀገራችን የሚፈፀመውን ኢ ሠብአዊ ድርጊት ለዓለም ጆሮ ለማድረስ ነው ›› በማለት የገልፀዋል ፡፡

Oromo

‹‹ ሁላችንም ወደ ልቦናችን ተመልሰን በአንድነትና በጋራ በመቆም ለነፃነታችን እንድንታገል ሞረሽ ወገኔ ለኢትዮጵያ ህዝብ ጥሪውን ያስተላልፋል›› ያሉት ወ/ሮ ዘውዲቱ ‹‹ በሀገር ቤት ሆነው ወያኔ በየጊዜው ለሚያፈናቅላቸው ፣ለሚያሳድዳቸው ወገኖች በሙሉ ግባችን አንድ ኢትዮጵያ እስከሆነች ድረስ ትግሉ የጋራ ነውና እኛም ከጎናቹ እንደምንሆን ፤እናንተም ከጎናችን እንድትቆሙ ጥሪ እናቀርባለን ›› ብለዋል ፡፡

በሠላማዊ ሰልፉ ላይ የተለያዩ መፈክሮች የተሰሙ ሲሆን የስዊዲን የግራ ዘመም ፓርቲ ተወካይም ስለኢትዮጵያ ወቅታዊ ሁኔታ ንግግር አድርገዋል፡፡

በቦስተን የትግራይ ክልል ም/ል ፕሬዝዳንት የጠራው ስብሰባ ተበጥብጦ ተበተነ |ሕዝቡ ወንበር ተወራወረ |ቪዲዮ ይዘናል

$
0
0


(ዘ-ሐበሻ) በሃገር ቤት በአማራ እና በኦሮሚያ የተቀጣጠለው የሕዝብ ቁጣ በውጩ ዓለም በሚገኙ ኢትዮጵያውያን ዘንድም በ እጅጉ እየተንጸባረቀ ነው:: ዛሬ በቦስተን የትግራይ ክልል ፕሬዚዳንት አምባሳደር አዲስ አለም ባሌማ የትግራይ ተወላጆችን ጠርተው ለማነጋገር ያዘጋጁት ሰብሰባ ኢትዮጵያውያን ሄደው በተቃውሞ እንዲበተን አድርገውታል::
TPLF Boston

በቦስተን የሚገኙ የዘ-ሐበሻ ዘጋቢዎች እንዳስታወቁት የትግራይ ክልል ምክትል ፕሬዚዳንት የትግራይ ተወላጆችን ብቻ መርጠው በቦስተን ስብሰባ የጠሩት በፖስተር ላይ 4 ሰዓት ላይ ቢሆንም ስብሰባውን ግን ቀደም ብለው 2 ሰዓት ላይ ጀምረውታል:: ይህም የሕዝብን ተቃውሞ ለመሸሽና ፖስተር አይተው የሚመጡ ተቃዋሚዎችን ለመሸሽ ቢሆንም ተቃዋሚዎች ግን 3 ሰዓት ላይ ሄደው ስብሰባው ላይ አቶ አዲስዓለም ባሌማን ተጋፍጠዋቸዋል:: ከውስጥ የነበሩት የትግራይ ተወላጆች ወደ ተቃውሚዎቹ ላይ ወንበር የወረወሩ ሲሆን ከተቃዋሚውም ወገን አጸፋውን እንደተሰጠና ስብሰባው ፖሊስ ደርሶ በአስለሽ ጭስ እንደተበተነ የዘ-ሐበሻ ምንጮች ገልጸዋል::

ፖሊስ የወንበር ውርወራውን ካስቆመ በኋላ የአቶ አዲስ ዓለም ባሌማ ስብሰባ እንዲቀጥልና ተቃውሚዎችም ከውጭ ሆነው እንዲቃወሙ ቢያዝም ተቃውሞው እጅግ እየበረታ በመሄዱ ፖሊስ ስብሰባው እንዲቋረጥና አዲስ ዓለም ባሌማም በቦስተን ተዋርደው እንዲሄዱ ሆኗል::

በተቃውሞው ላይ ከነበሩ ወገኖች ዘ-ሐበሻ ያነጋገረቻቸው የአይን እማኞች እንደገለጹት ለመቃወም ከሄዱት መካከል አንዲት ሴት ልጅ በሕወሓት ደጋፊዎች ወንበር ተወርውሮባት ጉዳት ደርሶባታል:: ሕክምና እያደረገችም ትገኛለች::

የኢትዮጵያውያኑን ቁጣ ለማየት ቪዲዮውን ይመልከቱ::

የህብር ሬዲዮ  ነሐሴ 8 ቀን 2008 ፕሮግራም

$
0
0

habtamu05 < …እነሱ እሳትና ጭድ የሚሉት ለዓመታት እርስ በእርሱ አደባድበው ስልጣናቸው ላይ ለመቆየት የወጠኑት ሴራ ከሽፎ ዛሬ ጎንደር ላይ ባህር ዳር ላይና ደብረ ማርቆስ ላይ በኦሮሞ ወገኖቻችን ላይ የሚፈጸመውን ግፍ እንቃወማለን ብሎ የአማራ ሕዝብ መነሳቱ በኦሮሚያም በተደረገው ተቃውሞ ላይ አማራ ወገናችን ነው ማለቱ እንቅልፍ ነስቷቸዋል ።የተባበረ ትግላችን ይቀጥላል …> አቶ ሌንጮ ባቲ የኦሮሞ ዴሞክራሲያዊ ግንባር ከፍተኛ አመራር ከአርበኞች ግንቦት ሰባት ንቅናቄ ጋር ድርጅታቸው ስላደረገው አብሮ የመታገል ስምምነት ተጠይቀው ከሰጡት ምላሽ የተወሰደ (ቀሪውን ያዳምጡት)

<…ይሄ ለውጥ ለሁሉም የሚመጣ በዚያች አገር ላይ ዲሞክራሲያዊ ስርዓት እንዲገነባ የምናደርገው ትግል ነው… የኦሮሞና የአማራ ሕዝብ መተባበር ስርዓቱን እንቅልፍ መንሳቱን እያየን ነው። ትብብሩና የጋራ ትግሉ ለሁሉም ነጻነት የሚያመጣ ነው…>  አቶ ነአምን ዘለቀ የአርበኞች ግንቦት ሰባት ንቅናቄ ከፍተና አመራር ከኦሮሞ ዲሞክራሲያዊ ግንባር ጋር ድርጅታቸው ስላደረገው ስምምነት ከአቶ ሌንጮ ባቲ ጋር በጋራ ከሰጡት መግለጫ የተወሰደ(ቀሪውን ያዳምጡት)

<…ተቃዋሚዎች አሁን አጣዳፊ የሆኑትን እና ወደፊት ሊነሱ የሚገባቸውን ጉዳዮች በመለየት በጋራ መምከር መነጋገር አለባቸው…>  አክቲቪስት ገረሱ ቱፋ  በወቅታዊው ሁኔታ ላይ ለህብር ሬዲዮ ከአክቲቪስት መስፍን አማን ጋር ከሰጠው ቃለ መጠይቅ(ክፍል አንድ)

<…ተቃዋሚዎች በጋራ መነጋገር መጀመር አለባቸው። የተናጠል የድርድር ጥያቄ ራሳቸውን ለማዳከምና ስርዓቱ ዕድሜ እንዲገዛ የሚያደርግ በመሆኑ አማራጩ የሕዝቡን የለውጥ ጥያቄ የሚፈታ ሁሉን አቀፍ ድርድር ማድረግ እንዲደረግ መግፋት አለባቸው ሌላው ግን መረሳት የሌለበት…> አክቲቪስት መስፍን አማን በወቅታዊ ጉዳይ በጋራ ከሰጠን ቃለ መጠይቅ የተወሰደ(ቀሪውን ተከታተሉት)

<…ሕዝቡ እዛ አገር ላይ እየተባበረ ነው እኛ እዚህ በውጭ አገር ሕዝቡን መከተል አለብን።  ኦሮሞና አማራ በጋራ መቆም አለብን። የሚደረገው ትግል የትኛውንም ብሄር የሚያገል አይደለም። ኦሮሞ አያገልም…> አቶ ንጉሴ ርቂቱ በቬጋስ የኦሮሞ ኮሚኒቲ ሊቀመንበር በከተማው የሕወሃሀት ደጋፊዎች የጠሩት ስብሰባን ለመቃወም በወጡበት ወቅት ከሰጠን ማብራሪያ (ቀሪውን ያድምጡት)

<…በቬጋስ የምንገኝም ተቃዋሚዎች በጋራ ተባብረን ይሄ ስርዓት የሚፈጽመውን ግፍ መቃወምና ተባብረን መቆማችንን ማሳየት ጭምር አለብን …> አቶ እንዳልካቸው ካሳሁን በቬጋስ የጎንደር ሕብረት የህዝብ ግንኙነት ሀላፊ ኦገስት 24/2016 በቬጋስ ስለተጠራው የተቃውሞ ሰልፍ ከሰጠን ማብራሪያ(ቀሪውን ይከታተሉ)

ኢትዮጵያዊያን አትሌቶች በብራዚሉ/ሪዮ ዲጄኔሮ ኦሎምፒክ ላይ  ሰሞኑን ያሰመዘዘገቡት አሰገራሚ እና አሳፋሪ ገጠመኞች በአለማቀፋዊ የዜና  አውታሮች እይታ (ልዩ ጥንቅር) ሌሌችም

ዜናዎቻችን

ኮ/ል ዘውዱን የሕዝብ አደራ አለብን ለሕወሓት  አሳልፈን አንሰጥም ያሉ በጎንደር የብአዴን አመራሮች ከስልጣን ተነሱ

አርበኞች ግንቦት ሰባት ንቅናቄና የኦሮሞ ዴሞክራሲያዊ ግንባር የሕዝቡን የለውጥ ፍላጎት ተግባራዊ የማያደርግ  የተናጠል ድርድር እንዳማይቀበሉ ገለጹ

የሕወሓት/ ኢህ አዲግ አገዛዝ 2 የአሜሪካ ዘጋቢዎችን  ጨምሮ ሶስት የውጪ ሚዲያ  ጋዜጠኞችን ሰሞኑን አሰረ

ዶ/ር አረጋዊ በርሄ፣ጋዜጠኛ አብርሃ በላይን ጨምሮ የትግራይ ብሄር ተወላጅ ፖለቲከኞችና አክቲቪስቶች የሕወሓት/ኢህአዴግ አገዛዝ ወርዶ የሽግግር መንግስት እንዲቋቋም ጠየቁ

ምዕራባዊያኖች  ዜጎቹን በመግደል እና በማሸበር ላይ ለሚገኘው የሕወሓት/ኢህአዲግ  መንግስት  ጭካኔ ጆሮ ዳባ ልበስ በማለታቸው  ተብጠለጠሉ

በእስራኤል ውስጥ አንድ ኢትዮጵያኖችን የሚያገል ዘረኛ ማስታወቂያ ታላቅ ቁጣ ቀሰቀሰ

የአሜሪካው እጩ ፕ/ት ዶናል ትራምፕ “ፕ/ት ባራክ ኦባማ አሸባሪው አይሲስን ፈጥረዋል”በማለታቸው ብርቱ ትችት  ገጠማቸው

ስዊዘርላንድ በርካታ ኢትዮጵያዊያን ስደተኞች ድንበሯን አልፈው አንዳይሻገሩ አገደች

አሜሪካን ጨምሮ ምዕራባውያን ሽብርተኝነትን ለመዋጋት በሚል ብቻ ሕወሓት ኢህአዴግ በሕዝቡ ላይ የሚፈጽመውን ግፍ እያዩ እንዳላዩ መሆኑን እንዲያቆሙ ተጠየቀ

በሕቡ ስታገል ቆይቻለሁ ያለው የኢትዮጵያ ሕዝብ ብሄራዊ ፓርቲ ተቃዋሚዎች በጋራ እንዲተባበሩ ጥሪ አቀርባለሁ አለ

ሰሞኑን  በልብ ህመም ሞቱ የተባሉት የቀድሞው የደ/አፍሪካ ፕ/ት ታቦ ኢምቤኬ አ/አ ውስጥ በሽምግልና ላይ መሆናቸው ተገለጸ  ሌሎችም  

Hiber radio Las Vegas ይህ ህብር ሬድዮ _የወቅታዊ መረጃ ምንጭ ነው። ህብርሬድዮ በአቤኔዘር ኮሙኒኬሽን ሴንተር እየተዘጋጀ  ከላስ ቬጋስ ከተማ፣ ዘወትር ዕሁድበአካባቢው ሰዓት አቆጣጠር ከምሽቱ 630 ሰዓት እስከሰዓት በህብር ሬዲዮ ድህረገጽ ወይም በቀጥታ በስልክ ለማዳመጥ 712 -432-8451 መደወል ብቻ በቂ ነውበእንግሊዝ ለምትኖሩ 01405770140 በስልክ ማዳመጥ ይቻላል። ዘወትር በድህረገጻችን፣ googel app store Hiber Radio ወደ ስልክዎ በመጫን ካልሆነምበዘሐበሻ እንዲሁም በተጠቀሱት ስልኮች ማዳመጥ ይቻላል።

Hiber Radio: የኮ/ል ዘውዱ አደራ አለብን ያሉ የብአዴን አመራሮች ከስልጣናቸው ተነሱ –ኦዴፍና አ.ግንቦት 7 የሕዝብን ፍላጎት የማያሟላ የተናጠል ድርድር አንቀበልም አሉ –በእስራኤል ውስጥ አንድ ኢትዮጵያኖችን የሚያገል ዘረኛ ማስታወቂያ ታላቅ ቁጣ ቀሰቀሰ

$
0
0

habtamu05
የህብር ሬዲዮ ነሐሴ 8 ቀን 2008 ፕሮግራም

አቶ ሌንጮ ባቲ የኦሮሞ ዴሞክራሲያዊ ግንባር ከፍተኛ አመራር ከአርበኞች ግንቦት ሰባት ንቅናቄ ጋር ድርጅታቸው ስላደረገው አብሮ የመታገል ስምምነት ተጠይቀው ከሰጡት ምላሽ የተወሰደ (ቀሪውን ያዳምጡት)

<...> አቶ ነአምን ዘለቀ የአርበኞች ግንቦት ሰባት ንቅናቄ ከፍተና አመራር ከኦሮሞ ዲሞክራሲያዊ ግንባር ጋር ድርጅታቸው ስላደረገው ስምምነት ከአቶ ሌንጮ ባቲ ጋር በጋራ ከሰጡት መግለጫ የተወሰደ(ቀሪውን ያዳምጡት)

<...> አክቲቪስት ገረሱ ቱፋ በወቅታዊው ሁኔታ ላይ ለህብር ሬዲዮ ከአክቲቪስት መስፍን አማን ጋር ከሰጠው ቃለ መጠይቅ(ክፍል አንድ)

<...> አክቲቪስት መስፍን አማን በወቅታዊ ጉዳይ በጋራ ከሰጠን ቃለ መጠይቅ የተወሰደ(ቀሪውን ተከታተሉት)

<...> አቶ ንጉሴ ርቂቱ በቬጋስ የኦሮሞ ኮሚኒቲ ሊቀመንበር በከተማው የሕወሃሀት ደጋፊዎች የጠሩት ስብሰባን ለመቃወም በወጡበት ወቅት ከሰጠን ማብራሪያ (ቀሪውን ያድምጡት)

<... ...> አቶ እንዳልካቸው ካሳሁን በቬጋስ የጎንደር ሕብረት የህዝብ ግንኙነት ሀላፊ ኦገስት 24/2016 በቬጋስ ስለተጠራው የተቃውሞ ሰልፍ ከሰጠን ማብራሪያ(ቀሪውን ይከታተሉ)

ኢትዮጵያዊያን አትሌቶች በብራዚሉ/ሪዮ ዲጄኔሮ ኦሎምፒክ ላይ ሰሞኑን ያሰመዘዘገቡት አሰገራሚ እና አሳፋሪ ገጠመኞች በአለማቀፋዊ የዜና አውታሮች እይታ (ልዩ ጥንቅር) ሌሌችም

ዜናዎቻችን

ኮ/ል ዘውዱን የሕዝብ አደራ አለብን ለሕወሓት አሳልፈን አንሰጥም ያሉ በጎንደር የብአዴን አመራሮች ከስልጣን ተነሱ

አርበኞች ግንቦት ሰባት ንቅናቄና የኦሮሞ ዴሞክራሲያዊ ግንባር የሕዝቡን የለውጥ ፍላጎት ተግባራዊ የማያደርግ የተናጠል ድርድር እንዳማይቀበሉ ገለጹ

የሕወሓት/ ኢህ አዲግ አገዛዝ 2 የአሜሪካ ዘጋቢዎችን ጨምሮ ሶስት የውጪ ሚዲያ ጋዜጠኞችን ሰሞኑን አሰረ

ዶ/ር አረጋዊ በርሄ፣ጋዜጠኛ አብርሃ በላይን ጨምሮ የትግራይ ብሄር ተወላጅ ፖለቲከኞችና አክቲቪስቶች የሕወሓት/ኢህአዴግ አገዛዝ ወርዶ የሽግግር መንግስት እንዲቋቋም ጠየቁ

ምዕራባዊያኖች ዜጎቹን በመግደል እና በማሸበር ላይ ለሚገኘው የሕወሓት/ኢህአዲግ መንግስት ጭካኔ ጆሮ ዳባ ልበስ በማለታቸው ተብጠለጠሉ

በእስራኤል ውስጥ አንድ ኢትዮጵያኖችን የሚያገል ዘረኛ ማስታወቂያ ታላቅ ቁጣ ቀሰቀሰ

የአሜሪካው እጩ ፕ/ት ዶናል ትራምፕ “ፕ/ት ባራክ ኦባማ አሸባሪው አይሲስን ፈጥረዋል”በማለታቸው ብርቱ ትችት ገጠማቸው

ስዊዘርላንድ በርካታ ኢትዮጵያዊያን ስደተኞች ድንበሯን አልፈው አንዳይሻገሩ አገደች

አሜሪካን ጨምሮ ምዕራባውያን ሽብርተኝነትን ለመዋጋት በሚል ብቻ ሕወሓት ኢህአዴግ በሕዝቡ ላይ የሚፈጽመውን ግፍ እያዩ እንዳላዩ መሆኑን እንዲያቆሙ ተጠየቀ

በሕቡ ስታገል ቆይቻለሁ ያለው የኢትዮጵያ ሕዝብ ብሄራዊ ፓርቲ ተቃዋሚዎች በጋራ እንዲተባበሩ ጥሪ አቀርባለሁ አለ

ሰሞኑን በልብ ህመም ሞቱ የተባሉት የቀድሞው የደ/አፍሪካ ፕ/ት ታቦ ኢምቤኬ አ/አ ውስጥ በሽምግልና ላይ መሆናቸው ተገለጸ ሌሎችም

የኢትዮጵያን ወቅታዊ ሁኔታ አስመልክቶ ከኦሮሞ ዲሞክራሲያዊ ግንባር ማዕከላዊ ኮሚቴ የተሰጠ መግለጫና የቀረበ ጥሪ

$
0
0

የኦሮሞ ዲሞክራሲያዊ ግንባር (ኦዲግ) ማዕከላዊ ኮሚቴ ስብሰባ ከሐምሌ 22 – 28 2008 ዓመተ ምህረት ድረስ ተካሂዷል፡፡ ይህን የአሁኑን የማዕከላዊ ኮሚቴ ስብሰባ ልዩ የሚያደርገዉ የኦሮሞ ሕዝብ በመላዉ ኦሮሚያ በሚያስደንቅ የአንድነት፣ የቆራጥነትና የጀግንነት ስሜት እያካሄደ ያለዉንና ለዘጠኝ ወራት የዘለቀዉን የነፃነት፣ የዲሞክራሲ፣ የእኩልነት፣ የሰብዓዊ መብት እና ራሱን በራሱ የማስተዳደር ጥያቄዎቹን እጅግ አጠናክሮ በቀጠለበት ታሪካዊ ወቅት የተካሄደ መሆኑ ነዉ፡፡ የኦዲግ ማዕከላዊ ኮሚቴ አባላት በመላዉ ኦሮሚያ የሚካሄደዉ ሰላማዊ የሕዝብ ተቃዉሞ በገዢዉ ቡድን የተደረጉበትንና የሚደረጉበትን አስከፊ ጫናዎችና የመሣሪያ አፈናዎች ሁሉ ተቋቁሞ ወደ ከፍተኛ ደረጃ እየተሸጋገረና በተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች የሚገኙ ሌሎች ኢትዮጵያዉያን ወገኖቹንም ለተመሣሣይ ትግል እያነሣሣ መሆኑን በአድናቆት እንመለከታለን፤ በሚቻለን መንገድ ሁሉም ለሰላማዊ ትግሉ ድጋፍ ለመስጠት ያለንን ቁርጠኝነት ደግመን ደጋግመን እናረጋግጣለን፡፡ ሕዝባችን የጠየቃቸዉን የዲሞክራሲ መብቶች ሙሉ በሙሉ እስኪጎናፀፍ ድረስ የተቃዉሞ እንቅስቃሴዉን አጠናክሮ እንደቀጥልም ልናበረታታዉ እንወዳለን፡፡

የኦሮሞ ዲሞክራሲያዊ ግንባር ማዕከላዊ ኮሚቴ ሰፊ ጊዜ በመዉሰድ ወቅታዊዉን የአገራችንን ሁኔታ በአጠቃላይ በመላዉ ኦሮሚያ እየተካሄደ ያለዉን ታሪካዊ የሆነ ሕዝባዊ የተቃዉሞ እንቅስቃሴ ደግሞ በተለይ እንደሚከተለዉ ገምግሟል፤

ODF

የኦሮሞ ሕዝብን ሰላማዊ የተቃዉሞ እንቅስቃሴ በተመለከተ፡-
በሕዝባዊ ወያኔ ሐርነት ትግራይ (ህወሐት) የሚመራዉ የኢሕአዴግ መንግሥት ላለፉት ሃያ-አምስት ዓመታት በብቸኝነት ሥልጣን ይዞ ቢቆይም ወይ ትክክለኛ ዲሞክራሲያዊ ሥርዓት በአገሪቱ እንዲሰፍን አላደረገም፤ ወይንም ደግሞ ጧትና ማታ የሚመፃደቅበትን ልማትና ዕድገት አስገኝቶ ሕዝባችንን ከአስከፊ የድህነት ኑሮ ለማላቀቅ አልቻለም፡፡ ይልቁንም የሥርዓቱ የግፍና የጭቆና ድርጊቶች ከጊዜ ወደጊዜ እየተባባሱ በመምጣታቸዉና በአገሪቱ የሰፈነዉ የሕዝቦች ድህነት፣ መከራና ስቃይ ከምን ጊዜዉም በላይ እየከፋ በመምጣቱ የኢሕአዴግ የአገዛዝ ሥርዓት የመፈናቀል፣ የረሃብ፣ የስደት፣ የዘወትር ስጋት፣ የጉስቅልናና የአስከፊ ድህነት መገለጫ ሥርዓት ሆኗል፡፡ እንደሚታወቀዉ የኦሮሞን ሕዝብ ለተጠናከረና ካለማቋረጥ ለረዥም ጊዜ ለዘለቀ ሰላማዊ የአመፅ እንቅስቃሴ ያነሣሣዉ ይህ ከልክ ያለፈ የኢሕአዴግ የግፍ አገዛዝ ሥርዓት ነዉ፡፡ የህወሐት/ኢሕአዴግ ሥርዓት በፈጠራቸዉ ችግሮች የተጎዳዉና ግንባር ቀደም ተጠቂ የሆነዉ የኦሮሞ ሕዝብ ብቻ ባለመሆኑም የተቃዉሞ እንቅስቃሴዉ ወደተለያዩ የአገራችን ክልሎች በመስፋፋት አገር-አቀፍ አመፅ ከመሆን ደረጃ ላይ እየደረሰ ይገኛል፡፡ ሕዝባዊ ተቃዉሞዉ በኦሮሚያ ክልል ተጠናክሮ በመቀጠል ወደሌሎች የአገራችን ክፍሎችም ቢስፋፋም ከገዢዉ ቡድን የሚሰጠዉ መልስ እንደተለመደዉ በጉልበትና በጦር መሣሪያ ለማፈን ከመሞከር ያለፈ ሆኖ አልታየም፡፡ የሕዝብን ስቃይና መከራ ለማስወገድ ሳይሆን ለራሳቸዉ ድሎትና ለተሠማሩበት የሕዝብ ሀብት ዝርፊያ ብቻ ቅድሚያ የሚሠጡት የገዢዉ ቡድን ቁንጮዎች ግን ለሕዝባችን ጥያቆዎች ተገቢዉን መልስ መስጠት አልቻሉም ወይም አልፈለጉም፡፡ ይልቁንም እስከአፍንጫዉ የታጠቀና ወገንተኝነቱን ለሕዝቡ ሳይሆን ለገዢዉ ቡድን ብቻ ያደረገ ገዳይና ጨፍጫፊ ሠራዊት አሠማርተዉ የብዙ ሺህዎችን ደም ማፍሰስ፣ የብዙ መቶዎችን ሕይወት ማጥፋትና በብዙ ሺህዎች የሚቆጠሩትን ደግሞ በጅምላ እስር ቤት ማጎርን እንደመፍትሄ አድርገዉ ወስደዋል፡፡ ይህ የገዢዉ ቡድን ጭፍንነት ደግሞ ሕዝባችን በልበ-ሙሉነት የጀመረዉንና በሚያስደንቅ ቆራጥነት ላለፉት ዘጠኝ ወራት ያካሄደዉን ሰላማዊ የተቃዉሞ እንቅስቃሴ አጠናክሮ እንዲቀጥል እየደረገዉ ስለሆነ በዚያች አገር የመንግሥት ሥርዓት ለዉጥ መምጣቱ አይቀሬ መሆኑን ያረጋገጠ ሂደት ሆኗል፡፡ ስለሆነም የኦሮሞን ሕዝብ በርታ፣ ሰላማዊ የተቃዉሞ ትግልህን አጠናክረህ ቀጥል፣ እኛም በተቻለን ሁሉ ከጎንህ ነን፤ በገዢዉ ቡድን “የከፋፍሎ መግዛት” ዕኩይ ፖሊሲ ተታለህ ከሌሎች ኢትዮጵያዉያን ወገኖችህ ጋር ምንም ዓይነት አለአስፈላጊ ቅራኔ ዉስጥ ላለመግባት እስከአሁን እንዳደረከዉ ሁሉ ለወደፊቱም ተገቢዉን ጥንቃቄ ሁሉ አድርግ እንላለን፡፡

የጎንደርን ሕዝብ የተቃዉሞ እንቅስቃሴ በተመለከተ፡-
ከዘጠኝ ወራት በፊት በመላዉ ኦሮሚያ የተቀጣጠለዉ ሕዝባዊ የተቃዉሞ እንቅስቃሴ በአገራችን ትክክለኛ ዲሞክራሲያዊ ሥርዓት ለማምጣት በሚካሄደዉ ሕዝባዊ ትግል ዉስጥ የኦሮሞ ሕዝብ ግንባር-ቀደም ሥፍራ እንዲይዝ ከማድረጉም በላይ ለሌሎች ኢትዮጵያዉያን ወገኖቹም በጥሩ አርዓያነት የሚታይ ስለሆነ የተለያዩ ሕዝባዊ የተቃዉሞ እንቅስቃሴዎች በተለያዩ የአገራችን ክፍሎች እንዲቀጣጠሉ ምክንያት ሆኗል፡፡ ጎንደር ዉስጥ በቅርቡ የተጀመረዉ ሕዝባዊ እንቅስቃሴም ለሕዝብ ፍላጎትና ምርጫ ተገዢ የሆነና ለመብት ጥያቄዎች ተገቢ የሆነ አፋጣኝ መልስ የሚሠጥ ትክክለኛ ዲሞክራሲያዊ ሥርዓት ለማምጣት እየተደረጉ ያሉ ሕዝባዊ እንቅስቃሴዎች አካል ነዉ፡፡ የጎንደርን ሕዝብ ጥያቄ ታሪካዊ ከሚያደርጉትና የሌሎች የኢትዮጵያ ሕዝቦች ሰላማዊ የመብት ትግል አካል መሆኑን ከሚያረጋግጡት እርምጃዎች አንዱ ጀግናዉ የጎንደር ሕዝብ ከመነሻዉ በኦሮሞ ወገኖቹ ላይ በገዢዉ ቡድን የተወሰደዉን ኢሰብዓዊ እርምጃ ማዉገዙና የፈሰሰዉ የኦሮሞ ሕዝብ ደም ደሙ፣ ያለፈዉ የኦሮሞ ታጋዮች ሕይወትም ሕይወቱ መሆኑን መግለፁ፤ የኦሮሞ ሕዝብ ጥያቄም የራሱ ጥያቄ አካል መሆኑን በማያሻማ ሁኔታ ማረጋገጡ ነዉ፡፡ የዚህ ዓይነቱ የሕዝቦች የትግል አንድነትና አጋርነት በሰላማዊ ሕዝባዊ አመፅ አማካይነት መገለፅ ሕዝባችንን ከምን ጊዜዉም በላይ በተጠናከረ መንገድ ከማስተሣሠሩም በላይ የተጀመረዉ ሕዝባዊ የተቃዉሞ እንቅስቃሴ ተጠናክሮ በሁሉም የኢትዮጵያ ማዕዘናት እንዲስፋፋ የሚያደርግ በመሆኑ የጎንደርን ሕዝብ ሰላማዊ የሆነ የዲሞክራሲ ትግል እጅግ ታሪካዊና የሚመሰገን ጅምር ያደርገዋል፡፡ እኛ የኦሮሞ ዲሞክራሲያዊ ግንባር ማዕከላዊ ኮሚቴ አባላትም ለጀግናዉ የጎንደር ሕዝብ እንቅስቃሴ ያለንን ልባዊ አድናቆትና አክብሮት እየገለፅን የተጀመረዉ ሰላማዊ የአመፅ እንቅስቃሴ ሕዝቡ የሚፈልገዉን ዉጤት እስኪያስገኝ ድረስ በሚቻለን ሁሉ ከጎኑ እንቆማለን፡፡ በዚህ አጋጣሚም ነፃነት፣ እኩልነትና ዲሞክራሲን ናፋቂ የሆናችሁ የኢትዮጵያ ሕዝቦች በሕወሐት/ኢሕአዴግ የከፋፍለህ ግዛ ፖሊሲ ሳትዘናጉ በጋራ በመቆም ይህን የሁሉም ችግሮቻችን ምንጭ የሆነዉን ጨቋኝ ሥርዓት ከሥሩ ለመገርሰስና በሥርዓቱ ጭፍን አከሄድ ምክንያት የተፈጠሩት ዘርፈ-ብዙ ችግሮች በሕዝባዊ ትግል ተወግደዉ ወደማይቀርላቸዉ መቃብር እንዲወርዱ ለማድረግ ከምንጊዜዉም በላይ እንድትተባበሩና በአንድነት እንድትቆሙ ወገናዊ ጥሪያችንን እናቀርብላችኋለን፡፡

አገር-አቀፍ የፖለቲካ ድርጅቶች ህብረት መመሥረትን በሚመለከት፡-
የኦዲግ ማዕከላዊ ኮሚቴ ከተለያዩ ተቃዋሚ የፖለቲካ ድርጅቶች ጋር ትብብር ለመመሥረት ይቻል ዘንድ በድርጅቱ የሥራ አስፈፃሚ አካል የተደረጉትን ጥረቶችና የተገኙትን አበረታች ዉጤቶች በጥልቀት ገምግሟል፡፡ እስከአሁን የተደረጉት ጥረቶችና የተገኙትም ዉጤቶች አበረታች ብቻ ሳይሆኑ ወደምንፈልገዉ ዲሞክራሲያዊ ሥርዓት ለመረማመድ ተስፋ ሰጪዎችም ናቸዉ፡፡ ስለሆነም የድርጅታችን የሥራ አሰፈፃሚ ኮሚቴ የተጀመሩትን ጥረቶች አጠናክሮ እንዲቀጥል፣ በአገር ዉስጥ እየተካሄዱ ያሉት ሰላማዊ የተቃዉሞ እንቅስቃሴዎች ተጠናክረዉ እንዲቀጥሉ ለማድረግ ይቻል ዘንድም የተጀመረዉን ከልዩ ልዩ የፖለቲካ ድርጅች ጋር ትብብር ለመመሥረት ያስቻለ ጥረት የበለጠ በማስፋትም አንድ ጠንካራ ኢትዮጵያ-አቀፍ የተቃዋሚ ኃይሎች ህብረት ለመመሥረት የሚያስችሉ እርምጃዎችን እንዲወስድ ሙሉ ኃላፊነት ሰጥተነዋል፡፡ ትክክለኛ ዲሞክራሲያዊ ሥርዓትን በኢትዮጵያ ዕዉን ለማድረግ በተለያዩ መንገዶች ትግል እያካሄዱ ያሉትን ተቃዋሚ የፖለቲካ ድርጅቶች ያሰባሰበ አንድ አገር-አቀፍ የተቃዋሚዎች ትብብር በአስቸኳይ መመሥረት እየተካሄደ ያለዉን ሕዝባዊ ተቃዉሞ የበለጠ ለማጠናከርና ለትግሉ የተማከለ የፖለቲካ አመራር ለመስጠት ከማስቻሉም በላይ የሕወሐት/ኢሕአዴግ መዉደቅ አይቀሬ በመሆኑ ለሰላማዊ ዲሞክራሲያዊ ሽግግር መሠረት ለመጣልም እጅግ በጣም አስፈላጊ ነዉ፡፡

ሰፊ መሠረት ያለዉና አገር-አቀፍ የሆነ የተቃዋሚ ድርጅቶች ህብረት ለመመሥረት ይቻል ዘንድ በኦሮሞ ዲሞክራሲያዊ ግንባር በኩል ረዥም ጊዜ የወሰዱ ተስፋ ሰጪ እንቅስቃሴዎች ሲደረጉ የቆዩ ሲሆን የእነዚህ እንቅስቃሴዎችና ጥረቶች ዉጤትም በቅርብ ጊዜ ለመላዉ የኢትዮጵያ ሕዝቦች ይፋ እንደሚደረግ ስናበስር ከፍተኛ ደስታ ይሰማናል፡፡ በዚህ አጋጣሚም የኢትዮጵያ ጉዳይ ይመለከተናል የምትሉ ድርጅቶች ሁሉ አሁን አገር ዉስጥ እየተካሄዱ ያሉትን ሕዝባዊ እንቅስቃሴዎች በቅርበት እንድትከታተሉና የሕወሐት/ኢሕአዴግን በሕዝባዊ ትግል መዉደቅ ተከትሎ ሊፈጠር የሚችለዉን ክፍተት ለመሙላትና አገራችን ወደአስከፊ ብጥብጥና ደም መፋሰስ እንዳትገባ ለማድረግ እንዲቻል እየተፈጠረ ወዳለዉ አገር-አቀፍ የፖለቲካ ድርጅቶች ህብረት በመምጣት የበኩላችሁን አስተዋፅኦ እንድታደርጉ ወገናዊ ጥሪያችንን እናቀርብላችኋለን፡፡

እንደ ኦዲግ እምነት የኢትዮጵያ መንግሥት ተቃዋሚ ኃይሎች ልዩነቶቻችንን አቻችለን በሚያግባቡን ዓላማዎች ሥር ብንሰባሰብና የተባበረ ትግል ማካሄድ ብንችል ያለምንም ጥርጥር እናሸንፋለን፤ እንደ የእስከአሁኑ አካሄዳችን የየራሳችንን መንገድ ብቻ ተከትለን በተበታተነ ሁኔታ እንቀጥል የምንል ከሆነ ግን መሸነፍ ብቻ ሳይሆን እንታገልለታለን የምንለዉን ሕዝብም ሆነ የጋራ ቤታችን ናት የምንላትን አገር ለከፋ ችግር እንዳርጋለን፡፡ ይህ ደግሞ ሁላችንንም የታሪክ ተጠያቂ እንድንሆን ያደርገናል፡፡ ከላይ እንዳልነዉ የሕወሐት/ኢሕአዴግ አገዛዝ መዉደቅ አይቀሬ ነዉ፡፡ አሁን ያለዉ ጥያቄ “የሕወሐት/ኢሕአዴግ መንግሥት ይወድቅ ይሆን?” የሚል ሳይሆን “መቼ ይወድቃል?” የሚለዉ ነዉ፡፡ በኦሮሚያ ተጀምሮ በተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች እየተስፋፋ ያለዉ ሕዝባዊ አመፅ ተጠናክሮ ከቀጠለ የዚህ ግፈኛ ሥርዓት መዉደቂያ ጊዜ ረዥም ስለማይሆን ይህን የታሪክ አጋጣሚ በሚገባ ለመጠቀም መዘጋጀት ይኖርብናል፡፡

ሁላችንም እንደምናስታዉሰዉ በአገራችን እንዲገነባ የምንፈልገዉን ዓይነት እዉነተኛ ዲሞክራሲያዊ ሥርዓት ለመገንባት ያስችሉ የነበሩ ብዙ የታሪክ አጋጣሚዎች አምልጠዉናል፡፡ በሕዝቦቻችን የደምና የሕይወት መስዋዕትነት የምንፈልገዉን ለዉጥ ሊያመጣ የተቃረበዉ ይህ የአሁኑ የታሪክ አጋጣሚ ግን በምንም ዓይነት መንገድ ሊያመልጠን አይገባም፡፡ ስለሆነም የኢትዮጵያ ጉዳይ ይመለከተናል የምንል ኃይሎች ሁሉ ጥቃቅን ልዩነቶቻችንን ወደጎን በመተዉ ተቀራርበን በመነጋገር በሚያስማሙን ጉዳዮቸ ላይ በጋራ ለመታገልና የሕዝባችንን መስዋዕትነት ፍሬያማ ለማድረግ የሚያስችሉንን ወሳኝ እርምጃዎች እንድንወስድ አጥብቀን እንጠይቃለን፡፡

የዓለም አቀፉን ማህበረሰብ በተመለከተ፡-
የኦዲግ ማዕከላዊ ኮሚቴ የዓለም አቀፍ ማህበረሰብ አባላት ለሕወሐት መራሹ የኢትዮጵያ ጨቋኝና ኢ-ዲሞክራሲያዊ መንግሥት የሚያደርጉትን የገንዘብም ሆነ የወታደራዊ መሣሪያዎች እርዳታ እንዲያቆሙ አጥብቆ ይጠይል፡፡ በተደጋጋሚ እንደታየዉ ሕወሐት መራሹ የኢትዮጵያ አምባገነን አገዛዝ በአገር ዉስጥ ምንም ዓይነት ሕዝባዊ መሠረትም ሆነ የሕዝብ ድጋፍ ስለሌለዉ በስልጣን ላይ ለመቆየት የሚያስችለዉን የገንዘብም ሆነ የወታደራዊ መሣሪያዎች ድጋፍ የሚያገኘዉ የአሜሪካን መንግሥት ጨምሮ ፅንፈኝነትን ለመዋጋት የአፍሪካ ቀንድ አካባቢን ትብብር ከሚፈልጉ የዓለም-አቀፍ ማህበረሰብ አባላት ነዉ፡፡ የአሜሪካ መንግሥትም ሆነ ሌሎች የምዕራብ አገራት መንግሥታት መገንዘብ ያለባቸዉ ከኢትዮጵያ ሕዝብ ጋር መቆም ሲገባቸዉ ከአምባገነን ጨቋኝ ገዢዎች ጋር በመቆም በየአገሮቻቸዉ የሚያራምዱትንና የሚያምኑበትን የዲሞክራሲ ሥርዓት እየተቃረኑ መሆናቸዉን ነዉ፡፡ ለዚህ ጨቋኝና አምባገነን መንግሥት የሚሠጡት ማንኛዉም ድጋፍም የአፍሪካ ቀንድ አካባቢን ሰላምና ፀጥታ ችግር ላይ የሚጥል መሆኑን ተገንዝበዉ ድጋፋቸዉን ለሕዝብ ቢያደርጉ በዚያ አካባቢ እንዲኖር የሚፈልጉትን ሰላምና ፀጥታ ዘላቂነት ባለዉ ሁኔታ ሊያረጋግጡ ይችላሉ፡፡ በተለይም የአሜሪካ መንግሥት ምንም ዓይነት የሕዝብ ድጋፍም ሆነ ተቀባይነት ከሌለዉ ከአምባገነኑ ሕወሐት መራሽ የኢሕአዴግ መንግሥት ጋር በመተባበር የራሱን የረዥም ጊዜ የሰላምና የፀጥታ ፍላጎት ለአደጋ ከመዳረግ ይልቅ የኢሕአዴግ መንግሥት ለሕዝቡ የዲሞክራሲ፣ የነፃነትና የሰብዓዊ መብት ጥያቄዎች ተገቢዉን መልስ እንዲሰጥ ጫና በማድረግ ከኢትዮጵያ ሕዝብ ጋር መቆም ይኖርበታል፡፡

በተደጋጋሚ እንደታየዉ ሕወሐት/ኢሕአዴግ የሚያዳምጠዉ አስተዳድረዋለሁ የሚለዉን ሕዝብ የልብ ትርታና የመብት ጥያቄ ሳይሆን የገንዘብም ሆነ የመሣሪያ ትራፊ የሚወረዉሩለትን ምዕራባዉያን መንግሥታት ስለሆነ የአሜሪካ መንግሥትና ሌሎች ምዕራባዉያን መንግሥታት የገንዘብና የወታደራዊ መሣሪያ ዕርዳታ በመስጠት ሕዝባችንን ከማስረገጥ ይልቅ በሥርዓቱ ዘንድ ያላቸዉን ተሰሚነት ተጠቅመዉ ገዢዉ ቡድን ለሕዝቡ ጥያቄዎች ተገቢ የሆኑ መልሶችን በአስቸኳይ እንዲሰጥ ጫና ሊያደርጉበት ይገባል፡፡ ለሕወሐት/ኢሕአዴግ መንግሥት ከአሜሪካም ሆነ ከሌሎች ምዕራባዉያን መንግሥታት የሚሰጠዉ የገንዘብም ሆነ የወታደራዊ መሣሪያ ዕርዳታም በጥንቃቄ መመርመር ይኖርበታል፡፡ ምክንያቱም የሚሰጠዉ የገንዘብም ሆነ የመሣሪያ እገዛ ገዢዉን ቡድን አጠናክሮ የኢትዮጵያን ሕዝብ ስቃይና መከራ ከማራዘም ዉጭ ለሕዝቡ የሚጠቅመዉ ነገር ስለሌለ ነዉ፡፡ ሰለሆነም ምናልባት ለተራቡ ወገኖቻችን የሚሠጥ የነፍስ ማዳን ዕርዳታ ካልሆነ በስተቀር አሁን በሥልጣን ላይ ላለዉ የኢትዮጵያ መንግሥት የሚሠጥ ማንኛዉም የገንዘብም ሆነ የመሣሪያ ዕርዳታ በአስቸኳይ እንዲቆም ጥሪያችንን እናቀርባለን፡፡

ፍትህና ነፃነት ለሁሉም ሕዝቦች!

የኦሮሞ ዲሞክራሲያዊ ግንባር ማዕከላዊ ኮሚቴ
ሐምሌ 28 ቀን 2008 ዓ. ም.

ታች አርማጭሆ ዶጋው በተባለ ቦታ አንድ ኦራል ሙሉ መከላከያ ወድሟል • ጎንደር ከተማ በቤት ውስጥ አድማ ተመታለች፤ ትግሬዎችን ከጎንደር ማስወጣት አሁንም ቀጥሏል

$
0
0

በባሕር ዳር አዲስ ዓለም ሆስፒታል 500 በላይ ሰዎች ታመው ሆስፒታል ገቡ
• አብዛኛዎቹ የዐማራ ከተሞች ከየት እንደመጡ በማይታወቁ ታጣቂዎች እንደሚጠበቁና ሕዝቡም ላይ ከፍተኛ በደል እየፈጸሙ ነው
• ጎንደር ከተማ በቤት ውስጥ አድማ ተመታለች፤ ትግሬዎችን ከጎንደር ማስወጣት አሁንም ቀጥሏል
• ታች አርማጭሆ ዶጋው በተባለ ቦታ አንድ ኦራል ሙሉ መከላከያ ወድሟል
• ዓለፋና ጣቁሳ የሚወራው ሁሉ የተጋነነ እንደሆነና በዐማራው ሕዝብ ላይ ጫና እንደፈጠረ ያነጋገርናቸው ሰዎች ገልጸዋል
• በመቄት በርካታ ወጣቶች ታስረዋል፤ ቆቦ አካባቢ ወታደሮች ላይ ጥቃት ደርሷል

ከሙሉቀን ተስፋው
ባሕር ዳር፤ በባሕር ዳር ከተማና አካባቢው ከ500 በላይ ሰዎች ታመው ዓባይ ማዶ አዲስ ዓለም ሆስፒታል መተኛታቸውን ከሆስፒታል አካባቢ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡ በመጠጥ ውኃ መበከል ችግር ‹‹አተት›› ለሚባል በሽታ ተዳርገዋል የተባሉት ሕሙማን አልጋ በመጥፋቱ ምክንያትም ድንኳን ተዘርግቶ ሕክምና ላይ መሆናቸው ታውቋል፡፡ የክልሉ መንግሥት መረጃው ወደ ውጭ እንዳይወጣ ከፍተኛ ጥንቃቄ እያደረገ እንደሆነ የሚናገሩት መረጃ ሰጪዎቻችን የበሽተኞች ቁጥር ከቀን ወደ ቀን መጨመሩን ነው የሚገልጹት፡፡ ቁጥራቸው ያልታወቁ ሰዎችም ሕይወት መጥፋቱን ተናገረዋል፡፡ የውኃው መበረዝ ከባሕር ዳር ከተማ የመጠጥ ውኃ ጋር የተያያዘ ይሁን አይሁን ግን በደንብ የተረጋገጠ ነገር የለም፡፡ አንዳንድ መረጃ ሰጪዎቻችን እንደሚሉት አንዳሳ እና ዓባይ ማዶ አካባቢ ነው የሚሉ ሲኖሩ ሌሎቹ ደግሞ ከከተማው የመጠጥ ውኃ ጋር የተያያዘ ሊሆን እንደሚችል አስተያየታቸውን ገልጸወዋል፡፡ ይህን ያክል የጤና ችግር ስለፈጠረው ጉዳይ የክልሉ ጤና ቢሮ ያወጣው ማስጠንቀቂያም ሆነ መግለጫ እንዳለ ያገኘነው ነገር የለም፡፡ የባሕር ዳር ከተማ ነዋሪዎች የሚጠጡት ውኃ ላይ ትኩረት እንዲያደርጉ በዚሁ አስተያየት ልሰጥ እንወዳለን፡፡

የጎንደር ከተማ (ፎቶ ፋይል)

የጎንደር ከተማ (ፎቶ ፋይል)

ጎንደር፤ የጎንደር ከተማ ዐማሮች ከትናንት ጀምሮ ቤታቸውን ዘግተው ተቀምጠዋል፡፡ መሥሪያ ቤትም ሆነ የንግድ ተቋም ምንም ዓይነት እንቅስቃሴ እንደሌለ ነው ዛሬ በስልክ ያረጋገጥነው፡፡ በጎንደር ከተማ ከሚገኙ መሥሪያ ቤቶች ሆስፒታል ብቻ አገልግሎት እንደሚሰጥ የታወቀ ሲሆን ምንም ዓይነት ተሸከርካሪም ሆነ እግረኛ ዝር እንዳላለ ነው የተገለጸው፡፡
በተያያዘም በጎንደር ከተማ የሚገኙ ትግሬዎች ማታ ማታ በቦይንግ አውሮፕላን የማስወጣቱ ሒደት እስካሁን እንደቀጠለ ነው የሚነገረው፡፡ እንደ መረጃ ሰጪዎቻችን ማታ ማታ መብራት እንዲጠፋ ይደረግና አውሮፕላን መጥቶ ትግሬወችን ይወስዳል ብለዋል፡፡ ለምን መብራት እንዲጠፋ አስፈለገ ብለን ላቀረብንላቸው ጥያቄ ‹‹ምናልባት እንዳይታዩ ካልሆነ በስተቀር እኛ የምናውቀው ጉዳይ የለም›› ብለዋል፡፡
ምዕራብ አርማጭሆ/ ጠገዴ፤ በምዕራብ አርማጭሆ ዶጋው እሚባለው አካባቢ ወደ ጋብላ ሰርገው ሊገቡ የነበረው የትግራይ ወታደሮችን የጫነ አንድ ኦራል ሙሉ ጦር ትናንት ከቀኑ 8፡00 አካባቢ መደምሰሱን ሰምተናል፡፡ በኦራሉ የነበሩ መከላከያዎች አንድም የተረፈ እንደሌለ ነው ከአሽሬ ያገኘነው መረጃ ያመለከተው፡፡
ይህ በዚህ እንዳለ በዳንሻ ከተማ ያሉ ትግራይ ተወላጆች ያላቸውን ዶሮ ሁሉ ሳይቀር ጭነው አካባቢያቸውን ለቀው እየሔዱ እንደሆነ ሰምተናል፡፡ ለምን ለቀው እንደሚሔዱ ለጠየቅናቸው ጥያቄ አካባቢውን ከትግሬዎች ነጻ ከሆነ በኋላ የዚህ አካባቢ ዐማራ በሙሉ ግንቦት ሰባት ነው በማለት ለማጥፋት እንዳሰቡ ከመጡት መከላከያዎች ሰምተናል ብለዋል፡፡ አስተያየት ሰጪዎቹ እንደሚሉት ዐማራውን በሙሉ ለመጨረስ መፈለጋቸው ነው እንጅ ዐማራው ከግንቦት ሰባት ጋር ምንም ዓይነት ንክኪ እንደሌለው ያውቃሉ ሲሉ ገልጸዋል፡፡ አንዳንድ የመከላከያ ሠራዊት አባላት በአብራጂራና አብደራፊ ከሕዝቡ ጋር ሲወያዩ ተነግሯቸው ከመጡበት ጉዳይ ጋር የሚመሳሰል ነገር ፈጽሞ ማግኘት እንዳልቻሉ ገልጸዋል ሲሉም አክለዋል፡፡ ትግሬዎችን ዐማራው እንዲወጡ ግፊት አላደረግም፤ ዐማራው አሁንም ሆደ ሰፊ እንደሆነ ነው፤ ዐማራው የሚለው ከአገዛዙ ጋር ሆናችሁ አትውጉን ነው ያለው ሲሉ አስተያየታቸውን ተናግረዋል፡፡
አለፋ/ጣቁሳ፤ በደልጊና በቁንዝላ አካባቢዎች ከፍተኛ ውጥረት ቢኖርም እንደሚወራው ወታደራዊ ግጭት እንደሌለ ከቦታው ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡ ከደልጊና ከቁንዝላ ከተሞች ያገኘናው ሰዎች እንደሚሉት ባለፈው ሳምንት በነበረው የዐማራ ተጋድሎ ከሁለቱም አካባቢዎች ሦስት ያክል ዐማሮች መስዋት ሆነዋል፡፡ አሁን ላይ ከተማዎቹ ከየት እንደመጡ በማይታወቁ ሰዎች እየተጠበቁ ነው ብለዋል፡፡ እነዚህ ሚሊሻዎች የከተማውን ሕዝብ አማረዋል ብለዋል፡፡ አያይዘውም በአካባቢው ገበሬው ከፍተኛ ጦርነት ነው የሚባለው ተጨማሪ መከላከያና ፖሊስ መጥቶ ሕዝቡን አደጋ እንዲያደርስበት በር ስለሚከፍት ያልተረጋገጠ መረጃ የሚያስተላልፉ አካለት እንዲያስቡበት ተናግረዋል፡፡

Meket City protesters

Meket City protesters

መቄት/ወልደያ፤ ቅዳሜ ምሽት ወደ ወልዲያ ከተማ ከትግራይ ሲመጡ የነበሩ ወታደሮች ላይ የሞትና የመቁሰል አደጋ መድረሱን ዛሬ ከመሸ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡ የቆሰሉ ወታደሮች ወልደያ ሆስፒታል በወታደሮች ጥበቃ ሕክምና እየተደረገላቸው እንደሚገኝ ብንሰማም ከሆስፒታል ምንጮች ግን ማረጋገጥ አልቻልንም፡፡ በተያያዘም የሰሜን ወሎዋ መቄት ከተማ ዐማሮች ትናንት ለተጋድሎ መውጣታቸውን ተከትሎ በጋሸናና በመቄት ከተሞች በርካታ ወጣቶች መታሰራቸውን ጠቁመዋል፡፡
አጠቃላይ፤ አብዛኛዎቹ የዐማራ ከተሞች ከየት እንደመጡ በማይታወቁ ቅጥረኛ ሚሊሻዎች እንደሚጠበቁ ለማወቅ ተችሏል፡፡ እነዚህ ሚሊሻዎች ከዐማራ ፖሊሶች ጋር ምንም ስምምነት የሌላቸው ሲሆን ማንኛውንም የማድረግ ስልጣን የፌደራል መንግሥት እንደሰጣቸው ታውቋል፡፡ ሰው ካያቸውም ለምን ታየኛለህ በማለት ከፍተኛ የአካል ጉዳት በየቦታው እያደረሱ እንደሆነ ነው የታወቀው፡፡ ከፍተኛ አበልና ማንኛውም ትጥቅ የተሟላላቸው እነዚህ ሚሊሻዎች ዐማሮችን ማማረራቸውን ገለጸው ሕዝቡን ግን ለበለጠ ትግል ማነሳሳታቸውን ጠቁመዋል፡፡

የኢትዮጵያ ትንሣኤ እንዴት? ከሸግግር መንግሰት እሰከ ጠብመንጃ አፈሙዝ!!!! –ግርማ ሠይፉ ማሩ

$
0
0

 

girmaseifu32@yahoo.com, www.girmaseifu.blogspot.com

Woyane

ኢትዮጵያችን ከሰሞኑ ድርስ የዲሞክራሲ እርጉዝ የሆነች ይመስላል፡፡ በሰላማዊ መንገድ ለውጥ ለምንፈልግ ሰዎች መንግሰት የፖለቲካ ማሻሻያ በማድረግ ሁላችንም አሸናፊ ሆነን የምንወጣበት ዲሞክራሲያዊ ስርዓት እናገኝ ይሆን ብለን እየጠበቅን ነው፡፡ የለም ገዢው ፓርቲ አብቅቶለታል በውስጥም በስብሷል ከውጭም ጫናው በርትቷል ፈንግለን እንጥለዋለን የሚሉም አሉ፡፡ ሌሎች ደግሞ አንድ ዓይነት ውጥረት ተፈጠረ በተባለ ቁጥር “የሸግግር መንግሰት” አቀንቃኞች ናቸው፡፡ እነዚህን ሶስት የዲሞክራሲ ፅንስ ማዋለጃ መንገዶችን በአጭር በአጭሩ ለማየት እሞክራለሁ፡፡ የግሌን አቋም የያዝኩበትን መስመር ትንሸ ሰፋ አድረጌ እምለከታለሁ፡፡

የሸግግር መንግሰት ማቋቋም

ይህን ሃሳብ የሚያቀነቅኑ ግለሰቦችም ሆኑ ቡድኖች ይህ ሃሳብ ተግባራዊ ሊሆን የሚችለው መቼ እንደሆነ የተረዱት አይመስለኝም፡፡ የዚህ ሃሳብ ተግባራዊ መሆን የሚችለው በኢህአዴግ መቃብር ላይ ብቻ ነው ብዬ ባልፍ በቂ ነበር፡፡ የኢህአዴግ መቃብር ደግሞ ከዚህ ቀጥሎ በምንመለከተው ሁኔታ የሚሆን ሰለሚሆን “የሽግግር መንግሸት” ለብቻው የሚቆም አማራጭ አይደለም፡፡ ገዢው ፓርቲ የሸግግር መንግስት ለሚባል አካል ስልጣኑን አስረክቦ ቢለቅ እኔም የምታዘበው ይመስለኛል፡፡ ጠቅላይ ሚኒሰትሩ ወግ ቢደርሳቸው የዚህን ያህል የተዓማኒነት ችግር ያለበት መንግሰት እየመራሁ ነው ከሚሉ፣ ፓርላማውም ወግ ደርሶች ጫና ቢያሳድር፣ “ፓርላማው”ን በትኖ አዲስ ምርጫ በህገ መንግሰቱ አንቀፅ 60 መሰረት እንዲከናወን ማድረግ ይችል ነበር፡፡ ለዚህ አልታደልም፡፡ ከዚህ የተለየ ህጋዊ ስርዓት “የሸግግር መንግሰት” ለመመስረት የሚስችል መንገድ የለም፡፡

በጣም ግልፅ ለመሆን ከዚህም ከዚያ በሚውጣጣ የቡድን እና ግለሰቦች ስብስብ “የሸግግር መንግስት” ይመስረት የሚሉ ሰዎች ያላቸውን የቡድን ውክልና ወይም ደግሞ ግለሰባዊ እውቅና መሰረት አድርገው ስልጣን በአቋራጭ የሚፈልጉ ናቸው፡፡ እመኑኝ እነዚህ ሰዎች በዚህ መስመር ሰልጣን ቢያገኙ ያገኙትን ስልጣን በቀጣይ በሚደረግ ምርጫ ስልጣናቸውን ቢያጡ አሜን ብለው የሚቀበሉ አይሆኑም፡፡ ሰለዚህ በእኔ እምነት “የሸግግር መንግስት ይቋቋም” በሚለው አልስማማ፡፡

ኢህአዴግ በስብሷል የስርዓት ለውጥ መደረግ አለበት

በዚህ ጉዳይ ኢህአዴጎች ባይስማሙ ብዙ ወገን ሊስማማ ይችላል፡፡ ይህን ስርዓት በስብሰሃልና ዞርበል እያልን ከሆነ በጉልበትና በጉልበት ብቻ የሚሆን ነው፡፡ ይህ ጉልበት ደግሞ አንድም በታጠቁ ኃይሎች፣ ወይም ደግሞ ህዝባዊ አመፅን ተከትሎ በሚመጣ የሰርዓት መፍረስ የሚገኝ ውጤት ነው፡፡ መንግሰት አሁን በያዘው ሁኔታ እሳቱን እያዳፈነ፣ የተዳፈነውን እሳት ግን ጭድ ስር እየደበቀ የሚቀጥል ከሆነ አይቀሬው ህዝባዊ ማዕበል እሳት ሆኖ ይበላዋል፡፡ ይህ እሳት ኢህአዴግን ብቻ ሳይሆን እኛም ከእሳቱ ብንተርፍ ወላፈኑ እይለቀንም፡፡ ይህ በሰላማዊ ሽግግር ሊታለፍ ካልቻለ ቀላል የማይባል ቀውስ በሀገራችን እንደሚያስከትል ግልፅ ነው፡፡ ይህ አማራጭ በትጥቅ የሚንቀሳቀሱ ኃይሎች እና ምንአልባት ህዝባዊ አመፅን በመምራት ላይ ያሉ ቡድኖች/ግለሰቦች በሚያደርጉት ስምምነት ቀጣይ የሀገሪቱ እጣ ፈንታ እንዴት ይሁን ብለው ሊነጋገሩ ይችላሉ፡፡ ኢህአዴግ-ሻቢያ- ኦነግ በለንደን እንዳደረጉት ማለት ነው፡፡ ከመንግሰት ጋር ይህ ውይይት ሊደረግ አይችልም፡፡ ሰለዚህ በዚህ አማራጭ ላይ ብዙ ማለት የሚቻል አይመሰለኝም፣ የአሸናፊዎች ፍትህ መስጫ ነው የሚሆነው፡፡ ምን አልባት በዚህ ወቅት እነዚህ አሸናፊ ኃይሎች የሚያቋቁሙት “የሸግግር መንግስት” አንደኛው ትክክለኛው አማራጭ የሚሆን ሲሆን እንደከዚህ ቀደሙ የኢህአዴግ የሽግግር መንግሰት መጪው የሸግግር መንግሰትም አግላይ ላለመሆኑ ምንም ዋስትና ሊኖረን አይችለም፡፡

ባጭሩ በሀይል የስርዓት ለውጥ ይደረግ ሲባል ኢህአዴግ ምንም ታሪክ እንደማይተርፈው መረዳት ያለበት ይሆናል፡፡ በሰፈረው ቁና መሰፈሩ ላይቀር የሚችልበት እድል ሰፊ ነው፡፡ ኢህአዴግ እና ኢህአዴጋዊያን ይህ ክፉ ቀን እንዳይመጣ ከዚህ ቀጥሎ የቀረበውን የፖለቲካ ማሻሻያ በማድረግ ሀገሪቱን ህዝብንም ሆነ እራሳቸውን እንዲጠብቁ መምከር እፈልጋለሁ፡፡

የፖለቲካ ማሻሻያ ማድረግ

አሁን ባለንበት ወቅት በሁሉም ወገን ተቀባይነት ማግኘት ያለበት ሃሣብ ነው ብዬ የማምነው፡፡ አሁን የደረስንበትን ቀውስ ሳናባብስ ነገር ግን ስር ነቀል የፖለቲካ ማሻሻያ በማድረግ ወደምንፈልገው ዲሞክራሲያው ስርዓት ልንሸጋገር እንችላለን የሚል እምነት አለኝ፡፡ ይህ የፖለቲካ ማሻሻያ የሚገኘው ግን አሁን የተጀመሩት ህዝባዊ እንቅስቃሴዎች ተጠናክረው ቀጥለው መንግሰት በልመና/በችሮታ የሚሰጠው ሳይሆን ለዚህች ሀገር መፍትሔ የሚያመጣ መንገድ ነው ብሎ አምኖ ሲቀበለው እና በሂደቱ በቅንነት ሲሳተፍ ነው፡፡ ከመንግሰት በተፃራሪ የቆምን ሀይሎችም የእኛ ብቻ ነው ልክ ከሚለው ግትር አቋም መለሳለስ ሲችሉ እና አንበረከክነው ከሚለው አስተሳሰብ ስንወጣ ነው፡፡

ይህ የፖለቲካ ማሻሻያ ለማድረግ በዋነኝነት ከመንግሰት ውጭ ያሉ ሀይሎች ችግሩ አሁን በስራ ላይ ያለው ህገመንግሰት ተቀዶ መጣል አለበት ከሚለው ፅንፍ ወጥተወ ሰላማዊ ሽግግር ለማድረግ እንደመነሻ የሚያገለግል እጅግ ጠቃሚ የሆነ የፖለቲካ ሰነድ መሆኑን አምኖ መቀበል ያስፈልጋል፡፡ ይህ ሲሆን ገዢው ፓርቲ በተለይ (የድል አጥቢያ አርበኞች ሳይሆኑ) በትግሉ ወቅት ከፍተኛ መስዋዕትነት የከፈሉበት ህገመንግሰት ተቀባይነት በማግኘቱ ደስተኞች ሰለሚሆኑ ሂደቱን የተሳካ ያደርገዋል፡፡ ይህም ሆኖ ህገመንግሰቱ ሊሻሻል የሚችል መሆኑ የማሻሻያ አንቀፆች ያሉት ስለሆነ በሂደት የሚሻሻልበት ሂደት መኖሩን መቀበል ደግሞ ለተቃዋሚዎች ተሰፋን የሚያጭር ይሆናል፡፡

ይህ የፖለቲካ ማሻሻያ በሚከናወንበት ጊዜ ሁሉ አሁን በስልጣን ላይ ያለው መንግሰት በመደበኛ የእለት ከእለት ስራው ላይ እንዲቆይ በመስማማት ሀገሪቱ ወደ ሌላ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ቀውስ እንዳትገባ በማድረግ በስልጣን ላይ ያሉትም ቢሆኑ በስልጣን ላይቀጥሉ ቢችሉ የሰነልቦና ዝግጅ ማድረጊያ ጊዜ ያገኛሉ፡፡ ከገዢው ፓርቲ ውጪ ያሉ በሀገር ውስጥም በውጭ የሚገኙ ስልጣን የሚፈልጉ ሀይሎችም ለስልጣን የሚያበቃቸውን በቂ ዝግጅት ከህዝቡ ጋር በማድረግ እራሳቸውን ለማዘጋጀት በቂ ጊዜ ያገኛሉ፡፡ ማን ስልጣኑን ይይዛል የሚለውን ህዝብ ይወስናል፡፡

የፖለቲካ ማሻሻያ ሂደቱን ሊመራ የሚችል ገለልተኛ የሆነ የሸግግር ሂደቱን የሚመራ “የሽግግር ኮሚሽን” የሚቋቋም ሲሆን ይህ ኮሚሽን በዋነኝነት በሀገሪቱ የፖለቲካ ምዕዳሩን ሊያሻሽሉ የሚችሉ ልዮልዮ ደንቦችን እና መመሪያዎችን እንዲወጡ በማድረግ፣ አፋኝ ህጎችን በመሻር/ወይም በምክር ቤቱ እንዲሻሩ በማድረግ ህዝቡ በፖለቲካው በንቃት እንዲሳተፍ ማድረግ ይጠበቅበታል፡፡

ይህ ማሻሻያ በልመና የሚገኝ ባለመሆኑ መንግሰት ወደ ትክክለኛውም አማረጭ እሲገባ ድረስ አሁን ያለው ህዝባዊ እንቢተኝነት እና “በቃ” የሚለው ህዝባዊ እንቅስቃሴ ተጠናክሮ እንዲቀጥል በማድረግ መንግሰት ይህን አስፈላጊ የፖለቲካ ማሻሻያ እንዲቀበል ማሰገደድ የግድ ይላል፡፡ ምንአልባትም መንግሰት በራሴ አፈታዋለሁ በሚል በሚጠራቸው “ህዝባዊ መድረኮች” ሁሉ በመገኘት ይህን የፖለቲካ ማሻሻያ እንዲያደርግ ግፊት ማድረግ ያስፈልጋል፡፡ መንግሰት “ሕዝባዊ” ብሎ የሚጠራች መድረኮች በአብዛኛው የፓርቲው አባላትና ጥቂት ጥቅመኞች እንደሆኑ በመረዳት በስብሰባው ላይ ሌሎች እንዲገኙ ጥረት ማድረግ ተገኝተውም ድምፃቸውን እንዲያሰሙ ማድረግ ያስፈልጋል፡፡

 

አሁን በመደረግ ላይ ያሉ እንቅስቃሴዎች መንግሰት ላይ የፈጠሩት ጫና ያለ ቢሆንም መንግሰት በተገቢው መንገድ ምላሻ ለመሰጠት በሚያስገድድ መልክ እንዳልሆኑ መገንዘብ ይቻላል፡፡ ለምሣሌ ሰላማዊ ሰልፍም ሆኖ ተቃውሞ በተደረገ ማግስት መንግሰት በዚህ ተቃውሞ ላይ የተሳተፉ ዜጎችን እየገደለና በየቤቱ እየዞረ እየለቀመ በማስር ከስራ በማፈናቀል እንቅስቃሴውን ማፈን እንደ አንድ ታክቲክ እየተጠቀመ ስለሆነ ማነኛውም የህዝብ ጥያቄ (ትክክል ባይሆን) ከመንግሰት ወገን መልስ ከመስጠት አልፎ ጥያቄውን በማቅረብ የተሳተፉ ወይም የመሩ ሰዎችን ማሰረን፣ ከስራ መባረርን መቃወም ሲከፋም እንዳይታሰሩ መከላከል፡፡ ከታሰሩም በታሰሩበት ቦታ በመገኘት ተቃውሞ መቀጠል፣ እስኪፈቱ ድረስ በፈረቃ በቦታው በመገኝት ተቃውሞ ከፍ እንዲል ማድረግ ያስፈልጋል፡፡

መንግሰት አሁን የግድ የሚያስፈልገውን የፖለቲካ ማሻሻያ እስኪቀበል ድረስ የተቀናጀ ህዝባዊ እንቅስቃሴ ማድረግ ህዝባዊ እንቅስቃሴው ከጊዜ ወደጊዜ አድማሱን እያሰፈ ረጅም ጊዜ የሚወሰድ የስራና ትምህርት ማቆም አድማ ማድረግ ሊጨምር ይችላል፡፡ መንግሰት በዚህ ላይ በሚሳተፉ ሰዎች ላይ በሚወሰድ እርምጅ በመቃውም ከላይ በተገለፀው መልኩ ተቃውሞን ማስፋት፡፡

በማነኛውም ጊዜ ሆነ ቦታ በሚደረጉ እንቅስቃሴዎች በማነኛውም ዜጋ ላይ ምንም ዓይነት ጉዳት እንዳይደርስ ጥንቃቄ ማድረግ፤በተለያየ ምክንያት የዚህ ዓይነት ችግሮች ሲፈጠሩ ማጋለጥና ህጋዊ እርምጃ እንዲወሰድ ህዝቡ እንዲተባበር ማድረግ፡፡ መንግሰት ይህን ሰበብ በማድረግ በሰው ህይወት ላይ አደጋ እንዳያደርስ፣ በሰው ህይውት ላይ ለሚደርሱ ጉዳቶች ሃላፊነቱን እንዲወሰድ ማድረግ፡፡

ኢትዮጵያዊያን በዘርና ሃይማኖት ተቧድነው ይጣላሉ ብሎ መገመት አስቸጋሪ ቢሆን መንግሰትን ጨምሮ የተለያዩ ሀይሎች ለቡድናዊ ፍላጎታቸው ማስፈፀሚያ አንድን የህብረተሰብ ክፍል እንደሰብዓዊ ከላለ ለመጠቀም መሞከራቸው አይቀርም፡፡ ማነኛውም ህዝባዊ እንቅስቃሴ በሚደረግበት ወቅት ከፍተኛ ጥንቃቄ ማድረግ እና ኢትዮጵያዊነታችን ከብሔር ማንነታችን ጋር በምንም ሁኔታ የማይጋጭ መሆኑን ማስመስከር ይጠበቅብናል፡፡ በተለይ ኢትዮጵያዊ ልሂቃን ይህን ጉዳይ ለፖለቲካ ጥቅም ከማዋል እራሳችንን በማራቅ ታሪክ መስራት ይጠበቅብናል፡፡


ሕመም፡- አንድም ለትምህርት፤ አንድም ለሞት! –ዲ/ን ዳንኤል ክብረት

$
0
0

unnamed (1)ጥንታውያን የአብነት ሊቃውንት፤ ‹ሕመም አንድም ለትምህርት፤ አንድም ለሞት ነው› ይላሉ። መታመሙን ላወቀ፣ መድኃኒቱን ለፈለገ፣ መድኃኒቱንም በትክክል ለወሰደ፣ ወስዶም ለዳነ ሰው ሕመም ለትምህርት ይሆነዋል፡፡ ሦስት ነገር ይማርበታልና፡፡ አንድም ዳግመኛ እንዳይዘው ጥንቃቄን፣ አንድም ቢይዘው ሊተርፍ የሚችልበትን መፍትሔ፣ አንድም ደግሞ ለሌላው የሚመክረው ልምድን ያተርፋል፡፡ ያለበለዚያ ግን የሕመም መጨረሻው ሞት ነውና ላንዱ ትምህርት የሆነው በሽታ፣ ሌላውን ይገድለዋል፡፡
አሁን ታመናል፡፡ ሕዝቡ የሚያነሣው ጥያቄ፣ መንግሥት የሚሰጠው ምላሽ፣ የሃይማኖት ‹አባቶች› የሚያወጡት መግለጫ፣ ማኅበራዊ ሚዲያው ከግራ ከቀኝ የሚያናፍሰው ነገር፣ ደጋፊና ተቃዋሚው ከወዲህ ወዲያ የሚሠናዘረው ዱላ፤ ሕመም ላይ መሆናችንን የሚገልጥ ነው፡፡ አሁን የሚያስፈልገን መታመሙን የሚያምን፣ መድኃኒቱን የሚፈልግና መድኃኒቱንም በተገቢው ሁኔታ የሚወስድ መንግሥትና ሕዝብ ነው፡፡
መጀመሪያ መተማመን የሚያስፈልገው ‹ችግር አለ ወይ?› የሚለው ላይ ነው፡፡ አዎን ችግር አለ፡፡ እየሆኑ ያሉት ነገሮች የሚነግሩን ችግር መኖሩን ነው፡፡ ችግሩ እነ እንትና ያነሣሡት፣ የቀሰቀሱት፣ ያደራጁት ምናምን ማለታችን ችግር መኖሩን አያስቀረውም። በሀገራችን ‹የጥያቄ ክፉ የለውም፤ የመልስ እንጂ›  ይባላል፡፡ የጥቂቶች ወይም የብዙዎች፣ የእነ አንቶኔ ወይም የነ እንትና መሆኑ ጥያቄውን አይለውጠውም። ለውጥ የሚያመጣው ለጥያቄው ተገቢውን መልስ መስጠቱ ነው። ‹በቅርቡ ያልመለሰ እረኛ፣ በሩቁ ሲባዝን ይውላል› እንደሚባለው፤ በየጊዜው ተገቢ መልስ ሳይሰጣቸው፣ ወይም ደግሞ ይዋሉ ይደሩ እየተባሉ፤ ያለበለዚያም የተፈቱ የመሰሉ ነገሮች እንደገና እያመረቀዙ መሆናቸው እየታየ ነው፡፡
በሽታው ምንድን ነው? ይኼ የምር የሆነ ውይይትና መግባባት የሚጠይቅ ነው፡፡ ለፖለቲካ ፍጆታ ወይም ለፕሮፓጋንዳ ወይም ለጊዜያዊ ድል ወይም የመሥዋዕት በግ ፍለጋ ወይም ለዶክመንተሪ ፊልም ወይም ደግሞ ለቁጣ ማብረጃ ከሚሆን ውይይት፣ መግለጫና ንግግር ያለፈ ሁሉን ዐቀፍ፣ ለመፍትሔ ብቻ የቆመና በእውነት የሚደረግን ውይይት የሚጠይቅ፡፡ አንድ ዓይነት ሰዎች ተሰብስበው አንድ ዓይነት ንግግር የሚናገሩበት ሳይሆን ልዩ ልዩ ፍላጎቶችን፣ አመለካከቶችን፣ አቋሞችንና የመፍትሔ ሐሳቦችን የሚወክሉ ወገኖች፤ ለአንዲት ሀገር ሲባል ሁሉን ዐቀፍ፣ ግን የምር የሆነ፣ ምናልባትም አንዳንዶቻችንን ሊመረን የሚችል መድኀኒት የሚፈልጉበት ውይይት ነው።  በተለመደው መንገድ መጓዛችንን ትተን አዲስ መድኃኒት በአዲስ መንገድ እንፈልግ፡፡ በተመሳሳይ መንገድ እየተጓዘ፣ የተለየ ውጤት የሚጠብቅ ሞኝ ብቻ ነውና፡፡
ከያቅጣጫው የሚሰጡ መግለጫዎች ሆድ ለባሰው ማጭድ የሚያውሱ፣ ከሚያረጋጉ ይልቅ የሚያናድዱ፣ ከሚያስታግሡ ይልቅ የሚያባብሱ፣ ከሚመክሩ ይልቅ የሚያነዝሩ ናቸው፡፡ ራሳቸው ችግር ናቸው እንጂ ችግር የሚፈቱ አይደሉም፡፡ ሌላው ቀርቶ የሃይማኖት አባቶች እንኳን የሚናገሩት ነገር ሃይማኖት ሃይማኖት የሚል አይደለም፡፡
አሁን የሚታየው የመሥዋዕት በግ ፍለጋ ነው። ማዶ ያሉትን አካላት የችግሩ መነሻና መድረሻ ማድረጉ መፍትሔ አያመጣም፡፡ እንዲያውም ጥያቄ ይፈጥራል፡፡ እዚህ አብረውት ከሚኖሩት የመንግሥት አካላት ይልቅ ማዶ ያሉትን ለምን ሰማ? እነዚያስ እዚህ ገብተው ሕዝብ እስኪቀሰቅሱ ድረስ እንዴት ዐቅም አገኙ? ሰው ውጭ ውጭ የሚያየው ቤቱ ምን ሲሆንበት ነው? መልሶ መላልሶ ችግሩ እዚሁ ነው የሚሆነው፡፡ የሚያዋጣው ወደገደለው መግባት ነው፡፡ ወደ ችግሩ፡፡
ቀጥሎ የሚነሣው ድግሞ ‹መድኃኒቱስ ምንድን ነው?› የሚለው ነው፡፡ ሁሉንም ወገኖች የሚወክለውና ለሀገሪቱ ሁነኛ መድኃኒት ለመፈለግ የሚደረገው የምር ውይይት ነው መድኃኒቱን ሊያመጣው የሚችለው፡፡
ከአንድ አቅጣጫ የሚመጣ መድኃኒት የሚያድንበት ጊዜ አብቅቷል፡፡ አሁን ሁሉን አግባብ፣ ሁሉንም ሊያድን የሚችል መድኃኒት የሚያስፈልግበት ጊዜ ላይ ነን፡፡ በዚህ ሂደት የሚፈራም የሚናቅም መኖር የለበትም፡፡ የሚገለል የሚጣልም መኖር የለበትም፡፡ መድኃኒት አንዳንድ ጊዜ የሚያስፈልግ እንጂ የሚፈለግ ላይሆን ይችላል፡፡ የሚያድን እንጂ የሚወደድ ላይሆን ይችላል፡፡ መድኃኒት ፍለጋው ይህንን ያገናዘበ መሆን አለበት፡፡ በዚህ ሂደት ልናድናት ቆርጠን መነሣት ያለብን ኢትዮጵያን ነው፡፡ ሥርዓቶች፣ ፖሊሲዎች፣ አደረጃጀቶች፣ አወቃቀሮች፣ ሊቀየሩ ይችሉ ይሆናል፡፡ ከጠላትነት ወደ ተነጋጋሪነት፣ ከአጥር ወደ ድልድይ፣ ከተጻራሪነት ወደ ተደጋጋፊነት መምጣት ያስፈልግ ይሆናል፡፡
በተበታተነ ሁኔታ በየአካባቢው የሚነዱትን እሳቶች ለማጥፋት ከመሯሯጥ ይልቅ ልብን ሰብሰብ አድርጎ የማያዳግም መፍትሔ መስጠቱ ነው የሚሻለው፡፡ በተለይም መንግሥት ይህ ይጠበቅበታል፡፡ እየሮጡ መስማት እየሮጡ መርሳትን ያመጣልና ቆም ብሎ ሰምቶ ቆም ብሎ መፍትሔ መስጠት ነው ብልሃቱ፡፡
ኮሶ ሲያሽር እየመረረ ነው፡፡ ወይ ሁላችን እናሸንፋለን፤ አለያም ሁላችንም እንሸነፋለን፡፡ ወይ ሁላችንም ለሕመሙ ትክክለኛውን መድኃኒት አግኝተን ተምረን እንድናለን፤ አለያም መድኃኒቱን አጥተን ሞተን እናርፋለን፡፡ ምርጫው ሁለት ነው። ሕመም አንድም ለትምህርት፣ አንድም ለሞት ነውና።
‹ሕመምተኛ ሲሻለው የዳነ ይመስለዋል፤ ሕመምተኛ ሲያቃዠው የሞተ ይመስለዋል› ይባላል፡፡ አንድ ነገር በትክክል መነሻው ሳይታወቅ፣ ችግሩም ሳይፈታ፣ በራሱ ጊዜ ጋብ አለ ማለት ሕመሙ ዳነ ማለት አይደለም፡፡ ብርድ እንዳገኘ የጉንፋን ቫይረስ ሁኔታው ሲመቻችለት እንደገና ይነሣል፡፡ ሕመምተኛው ሲሻለው የዳነ እየመሰለን ከምንተወው፣ በሚገባ ሕመሙን መርምረን ተገቢውን መድኃኒት መስጠቱ የተሻለ ነው፡፡ ዛሬ የተነሡት ነገሮች ጋብ ቢሉ እንኳን ባንድ በኩል ጥለውት የሚያልፉት ጠባሳ፣ በሌላ በኩል በትክክል ባለመፈታታቸው ምክንያት በባሰ ሁኔታ ዳግም መነሣታቸው አይቀሬ ነው፡፡ እንደምናየው ከሆነ በሀገሪቱ የሚከሰቱ ለውጦች የሰውን አስተሳሰብ፣ አነዋወር፣ መስተጋብርና አሰላለፍ እየለወጡት ነው። ዛሬ እንደትናንቱ የሆነ የለም፡፡ ነገም እንደዛሬ የሚሆን አይገኝም፡፡
በሌላ በኩል ደግሞ ‹በሽተኛ ሲያቃዠው የሞተ ይመስለዋል› እንደተባለው ሀገሪቱ ያለቀላት የሚመስላቸው ወገኖች፤ የሀገሪቱን ታሪክ የማያውቁ ብቻ ናቸው፡፡ ከዚህ የባሰ ችግርና መከራ፣ ከዚህ የባሰ ውጥንቅጥና ፈተና አሳልፋ የምትኖር ሀገር ናት፡፡ አሳልፋ የማታልፍ ሀገር ናት፡፡ በየዘመኑ ከሕመማቸው መማር ያልቻሉ መንግሥታትና ኃይላት አልፈዋል፡፡ ኢትዮጵያ ግን አሁንም አለች፡፡
ሕመሙን ከማባባስ፣ በሕመሙ ለማትረፍም ከመሮጥ፣ ሕመሙን በትክክል አክመን ከሕመሙ እኛው ተምረን እንውጣ፡፡ ካልሆነ ግን ሞተን ለሌሎች የታሪክ መማሪያ እንሆናለን፡፡

ከሀብታሙ አያሌው ጋር ዛሬ በጤናው እና በወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳይ ዙሪያ ስንጨዋወት አጽንኦት ሰጥቶ የተናገራቸው ጠንካራ ሀሳቦች -ኤልያስ ገብሩ ጎዳና

$
0
0
ሀብታሙ አያሌው

ሀብታሙ አያሌው

“በህዝብ ትግል የህወሃት ካምፕ ይፈርሳል፤ …አንድ በሆንን ማግስት ህወሃት እንደጥዋት ጤዛ እንደሚረግፍ አልጠራጥርም”
“የአማራውን ህዝብ እንደ ቅጥል ማርገፍ የጀመሩት ዛሬ አይደለም”
“የህወሃት ሰዎች እንደደርግ ወታደር ኮፊያቸውን ዘቅዝቀው የሚቆሙበትን መሬት በኦሮሚያ ተወላጆች ደም ስላጨማለቁት መጨረሻቸው እጅግ የከፋ እንደሚሆን ይሰማኛል”
“በዚህ ወቅት የትግራይ ህዝብ ይሄንን ጨቋኝ ስርዓት ነቅሎ ለመጣል የተለየ ታሪካዊ ሃላፊነት እንዳለበት ይሰማኛል”
ሃብታሙ አያሌው

/ከሀብታሙ አያሌው ጋር ዛሬ በጤናው እና በወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳይ ዙሪያ ስንጨዋወት አጽንኦት ሰጥቶ የተናገራቸው ጠንካራ ሀሳቦችን እንዲህ አሰናድቼዋለሁ/

“በኦሮሚያ እና በአማራ ክልሎች በሚገኙ በተለያዩ ቦታዎች በህወሃቶች ትዕዛዝ ሳቢያ በጥይት ተመትተው በሞቱ ወገኖቼ እጅግ ሲበዛ አዝኛለሁ። እነዚህ በግፍ በህወሃት የሞቱ ሰዎች በኢትዮጵያ ታሪክ ህያው ሰማዕት ሆነው ለዘላለም ይኖራሉ።
ወልቃይትን በሚመለከት፣ በእኔ እምነት ህዝቡ ማንነቱ እንዲረጋገጥለት ጥያቄ እያቀረብ መሆኑን አውቃለሁ። ይህን እንድረዳ ያደረገኝ አሁን የተደረገው አመጽ አይደለም። ህወሃት/ኢህአዴግ ጋር በነበርኩበት ጊዜ በከፍተኛ ምስጢር ይዞ ተግባራዊ ለማድረግ ሲንቀሳቀስ በታዘብኳቸው ጊዜ በድርጅቱ ላይ እምነት እንዳይኖረኝ ካደረጉ እኩይ ተግባሩ አንዱ የወልቃይት ጉዳይ ነበር።

የህወሃት የመስፋፋት ዘመቻ ወሎን፣ አፋርን፣ ወልቃይትን፤ አሁን ደግሞ ጎንደርንና ጎጃም ጋር ከሱዳን የሚዋሰኑበትን ሰፊ ድንበር እስከ ህዳሴው ድልድይ ድረስ አጠቃልሎ ታላቅ የሚሏትን ትግራይ ለመመስረት ያለመ ነበር። የአማራውን ህዝብ እንደቅጠል ማርገፍ የጀመሩት ዛሬ አይደለም። ይህንን ሴራ ከእነሱ ጋር እያለሁ ስለተረዳሁ ከዚያ የጥፋት ድርጅት ወጥቼ የቀድሞ አንድነት ለፍትህና ለዴሞክራሲ ፓርቲን በመቀላቀል በጎንደር ብቻ ሁለት ታላላቅ ሰልፎችን በመምራት እንዲህ የህዝቡ መብት እንዲከበር ብርቱ ጥረት አድርጌያለሁ። ድንበሩን/መሬቱን በተመለከተም ጥናት በማድረግ በአዲስ አበባ በፓርቲው አዳራሽ ጥናቱን ለህዝብ አቅርቤያለሁ።

የኦሮሚያ መሬት ከተማ በማስፋፋት ስም ህወሃቶች ሊቀራመቱት የያዙትን ዕቅድ የማውቅ በመሆኑ በአዲስ አበባ እና በኦሮሚያ የተለያዩ ከተሞች ሰላማዊ ሰልፎችን በመምራት ትልቅ ተቃውሞ ሳደርግ ነበር።

ስለዚህ አሁን የሚሰማኝ፣ በዚህ ወቅት ህዝቡ ለትግል ተነሳስቶ በህወሃት በአደባባይ ሲገደል አልጋ ላይ የወደኩ ደካማ ብሆንም በቁጭት ከማልቀስ በቀር ሀዘኔን የምገልጽበት ነገር አጥቻለሁ።

አንድ ነገር ግን እርግጠኛ ነኝ፣ በህዝብ ትግል የህወሃት ካምፕ ይፈራርሳል። የህወሃት ሰዎች እንደደርግ ወታደር ኮፍያቸውን ዘቅዝቀው ለመለመን የሚቆሙበት መሬትን እንኳን በኦሮሚያ ተወላጆች ደም ስላጨማለቁት መጨረሻቸው እጅግ የከፋ እንደሚሆን ይሰማኛል።

በዚህ ወቅት የትግራይ ህዝብ ይሄንን ጨቋኝ ስርዓት ነቅሎ ለመጣል የተለየ ታሪካዊ ሃላፊነት እንዳለበት ይሰማኛል።
አሁንም አላለሁ፣ እመነኝ ደርግ ወድቋል፣ ኢህአዴግም ይወድቃል። ድል የህዝብ ነው። በዚህ ታሪካዊ ወቅት አማራና ኦሮሞ ብቻ ሳይሆን የህወሃት አገዛዝ ለመጣል ሁሉም ኢትዮጵያዊ አንድ ሆኖ መቆም አለበት። አንድ በሆንን ማግስት ህወሃት እንደጥዋት ጤዛ እንደሚረግፍ አልጠራጥርም!

መታመሜን ተከትሎ በተለያየ መንገድ ከጎኔ ዛሬም ድረስ ለቆማችሁ በሙሉ ከልብ ዳግሜ ማመስገን እወዳለሁ። አሁን በቀን 400 ሚሊ ግራም ማደንዘዣ (ፔቲዲን) እየተወጋሁ ነው። በዚህ ሁኔታ እንዴት እንደምዘልቅ አላውቅም። ይህ ያሳስበኛል። ምን ያህል ሰውነቴን እንደሚጉዳው አላውቅም። ማደንዘዣው የጎንዮሽ ጉዳት አለው። ዛሬም ድረስ ሌላ ህክምና ስላላገኘሁ ሌላ ኢንፌክሽን ተፈጥሮ የባሰ ነገር እንዳይከሰት በመከላከል ላይ እገኛለሁ። በአብዛኛው ዐበል እና እምነት (ቅባ ቅዱስ) ነው የምጠቀመው።”

ጎንደር ለ3ኛ ቀን የሥራ ማቆም አድማው ቀጥሏል –ከተማው ጭር ብሏል

$
0
0
ከወር በፊት በጎንደር ከተማ የጀመረው ተቃውሞ ሰሞኑን እየተረጋጋ መሆኑን የክልሉ መንግስት ገልጾ ነበር፡፡ ይሁን እንጂ ዛሬ ደግሞ መልኩን ቀይሯል፡፡ አሁን እየተከናወነ ስላለው ከተማ አቀፍ አድማ መንግስታዊ አካላት እስከአሁን ያሉት ነገር ባይኖርም ትናንትና የተጠራው ከቤት ያለመውጣት ተቃውሞ ሶስት ቀናትን የሚቆይ እንደሆነ በከተማዋ ውስጥ የተሰራጨው የአድማ ጥሪ ወረቀት ይገልጻል፡፡ ዛሬም ጎንደር ለሁለተኛ ቀን ጭር ብላ መዋሏን ምንጮቻችን ከስፍራው ገልጸዋል፡፡
የከተማዋ የንግድ ተቋማት ተዘግተዋል፡፡ በፒያሳም ሆነ በአራዳ የሚገኙ የንግድ ሱቆች ዝግ ሆነዋል፡፡ የመንግስት ሰራተኞችም ወደ ስራ ገበታቸው እንዳልገቡ ነው ከስፍራው ያገኘንው መረጃ የሚጠቁመው፡፡ በተለየ መልኩ የትራንስፖርት አገልግሎት ሰጪ ተቋማት አድማውን መቀላቀላቸው ከተማዋን ጭር አድርጓታል፡፡
go 1 go2 go4 go6

13939608_10209957233958206_7978359749589309455_n

የአጋዚ ወታደሮች በኦሮሚያ አንዱን ወጣት ቤቱን ሰብረው ገብተው ገደሉት

$
0
0

(ዘ-ሐበሻ) 8ኛ ወሩን እያገባበደደ ወደ 9ኛው ወር እየተጠጋ ያለው የኦሮሞ ሕዝብ ትግል አሁንም እንደቀጠለ ሲሆን ከተሞች በአጋዚ ሰራዊት አሁንም እንደተከበቡ ይገኛሉ::

fajiso
እነዚህ የአጋዚ ወታደሮች ቤት ለቤት እየገቡ በየቀኑ ወጣቱን እየገደሉት እንደሆነ መረጃዎች ሲሰሙ ቢቆይም በፎቶ ግራፍ ሊደገፍ ባለመቻሉ በአብዛኛው ሳይዘገብ ቆይቷል:: ትናንት በምስራቅ ሸዋ ባቱ ከተማ የተፈጸመው ግን በፎቶም ተደግፎ በሶሻል ሚድያዎች ተለቋል::
በምስራቅ ሸዋ ባቱ ከተማ ነዋሪ የሆነው ወጣት ሆራ ፋጂሶ የአጋዚ ወታደሮች ቤቱን ሰብረው በመግባት እዚያው በተኛበት እንደገደሉት ጀዋር መሐመድ ከለቀቀው መረጃ ለመረዳት ተችሏል::

የማለዳ ወግ …ጭር ባለው የጎንደር ሰማይ ስር በዝምታ ህዝብ ሲያድም !

$
0
0

በመንገዱ … 
የማለዳ ወግ …ጭር ባለው የጎንደር ሰማይ ስር በዝምታ ህዝብ ሲያድም !
=========================================
* የተቆጣው ህዝብ …
* ስለተገደሉት ፤ ስለቆሰሉትና ስለታሰሩት ሀገሬው ከፍቶታል … 
* የተኛውን ” ኢትዮጵያዊ አንበሳ ” ቀስቅሰውታል …
* ሶስት ቀን የደፈነው የስራ የማቆም አድማ ሲከዎን… ! 

ነቢዩ ሲራክ

ዛሬ ትናንት አይደለም ፣ ትናንተም ዛሬ አይመጣም ። ኢትዮጵያና ህዝቧን ዛሬ እዚህ ያደረሰው መንገድ ፍጹም አድካሚና አሰልች ለመሆኑ አስረጅ ባሳለፍናቸው ወራት በኦሮምያ የተካሄደው መጠነ ሰፊ ተቃውሞና ሰሞነኛው የአማራና ተጋድሎ ማሳያ ናቸው ። ህዝብ አድልኦ ሲደረግበት “ይከበርልኝ ” ስለሚለው መብቱ ጥያቄ አቅርቦ መልስ ሲያጣ ነገር አለ ማለት ነው ! መብቱ ስላልተከበረለት ሲቆጣና ሲያምጽ ደግሞ አደጋ መኖሩ አያከራክርም ፣ ተበደልኩ ያለ ህዝብ በጠመንጃ አፈሙዝ ” ተመለስ “ ሲባል “አሻፈረኝ “ ይላል ! “ እንቢ አሻፈረኝ “ ሲል በጠብመንጃ ባሩድ ደም ሲፈስ ፤ ደሙ የመስዋዕትነት ደም ይሆናል ! ” ሐገር ተረካቢ እያልን ” የምናንቆለጳጵሳቸው ትንታግ ወጣቶች የ አደባባይ ወጥተው የወገናቸውን ምሬት ባስተጋቡ በወህኒ ታጉረው የመረረውን ጽዋ እየተጎነጩት ነው ፤ አሰቃቂ ድብደባ እየተፈጸመባቸው በመሆኑ የጎንደር አማራ በመቃዎም ከእሁድ ጀምሮ እስከ ዛሬ ተቃውሞውን በዝምታና ተቃውሞ የስራ ማቆም አድማ በመግለጽ ላይ ነው !

gonder

ባሳለፍናቸው ቀናት ጎንደር በዝምታ ተቃውሞ ሲናጥ ቀድሞ ደመቆ ይገማሸር የነበረው የፋሲል ከተማ አድማ መመታቱ እንደተሰማ ወፍ ዝር አለማለቱ እውነት ነው። ብዙ ያነጋገርኳቸው ነዋሪዎች ጸጥ ረጭ ባለው ተቃውሞ ሰማይ ስለተገደሉት ፤ ስለቆሰሉትና ስለታሰሩት ሀገሬው ከፍቶታል ፤ ተቃውሞው ደግሞ ሌላ ደም የሚገብርበት እንዳይሆን በማሰብ ወደ ዝምታ የስራ ማቆም አድማ ለቀናት ማካሄዱ መልዕክቱ የቁጣውን ክብደት ለሹሞች ማስየላለፍያ ነው የሚል አስተያየት በነዋሪው በኩል አስባስቤያለሁ ። የተቃውሞው መሪ ማን እንደሆነ ይታዎቃል ?ብየ መጠየቄ አልቀረም የማይፈሩት ወጣቶች መለሱ … ” አንተ ደግሞ ማን ይመራዋል ብለህ ነው ፤ በተለያየ መንገድ ወሽቀውት የነበረው ነዋሪ በሙሉ በአስገራሚ ሁኔታ አንድ ሆኗል ፤ ሀገሬው በአንድ ተስማምቶ ያወጣው በህዝቡ መካከል ይሰራጫል ፤ የተባለውን ሰው ሳይፈራ ይተገብራል ! በቃ ይህ ነው እየሆነ ያለው ። “ በማለት መረጃ አቀብለውኛል ። ሌላው የከተማው ነዋሪን ስለ ተቃውሞው እና በተዛማጅ ስላለው እንቅስቃሴ ጠይቆያቸው ” ከሁሉ የሚገርምህ የሀገርህ ሰው የሰራውን የሚያኮራ ስራ ልንገርህ ” በማለት በሶስት ቀኑ የስራ ማቆም የዝምታ ተቃውሞ የመንግስት መስሪያ ቤቶች ሳይቀር ዝግ እንደነበሩ ፤ ስራ ሰርተው በእለት ጉርስ ለሚተዳደሩት ነዋሪው በራሱ በመደራጀት በግልና በእድር ቀለብ እየሰፈረ ድጋፍ ያደረገላቸው በመጠቆም አስተያየያቸውን ሲቋጩ “ ህዝቡን በድለው ፤ ክብሩን ደፍረው ፤ ተቃውሞ የወጣነውን ሁላ አሸባሪ እያሉ አናድደው፤ እነሱ ወደማይመሩት ህብረት ቀላቅለውናል ፤ ድርጅት አይጠቅመንም ፤ እንዲያው በአጠቃላይ አሁን ያለው የመናበብ ህብረት ፈጽሞ በጎንደር ታይቶ አያውቅም ፤ በግፍ አቁስለው አንድ አድርገውናል ። “ ብለውኛል !

ሲናገሩ ወኔያቸው የሚሸንጠው አባትን ቀድሞ አውቃቸዋለሁ ፤ ደውየ መረጃ ጠየቅኩና ስማቸውን ግን እንደማልጠቅስ ላረጋግጥላቸው ስብተከተክ ንግግሬን አስቁመው እንዲህ ሲሉ እንቅጩን ነገሩኝ “ አልዋሽምና ስሜ አስፈላጊ ከሆነ ቢጠቀስ ችግር የለብኝም!” አሉኝ ! ገረመኝ ትንሽ ትልቁ ፍርሃትን አልፈራ ማለቱ ደነቀኝ ! እኔ ለደህንነታቸው ስል ስማቸውን መጥቀስ የማልፈልገው ይህ ታዋቂ የሃገር ሽማግሌን በሰጡኝ አስተያየት መንግስት እየወሰደ ባለው እርምጃ መቀየማቸውን ገልጸው ነዋሪው ግን ዘር ሳይለይ ባንድ ማበሩን እንዲህ በማለት ገልጸውኛል “… አማራ በየቦታው ሲገፋ ትንፍሽ ያላሉት በግርግሩ ከተጎዱት መካከል ጥቂት የትግራይ ተወላጆች ንብረት ተጎዳ ብሎው ማላዘናቸው ተገቢ አልነበረም ። የአማራው ንብረትም ክእነሱ በላይ ተጎድቷል ፤ የእነሱስ ንብረት ነው ፤ የእኛ ልጆችም እኮ ተቀጥፈዋል ? ለምን ይህን እኩል አያዩትም ወደዛ አልገባም ! አሁን ቂም እንዳንቃባ በሚል ሌላው ቀርቶ በከተማችን የሚገኙ የትግራይ ወገኖቻችን በተቃውሞው ስጋት እንዳያድርባቸው መክረናል። በከተማው ያሉ ተቋሞችን ማንም እንዳያጠቃ ተደርጓል ። ተንኮለኛ ሰርጎ ገብቶ እንዳያጠቃም ሰው እንደሚጠብቅ ተስማምቷል ” በማለት ዘርዘር ያለ መረጃ አቀብለውኛል !

መቸም የሚገዙትን ማህበረሰብ አስተሳሰብ የማይረዱ ያልታደሉ ናቸው ! ያን ሰሞን እየተበደለና እየተገፋ ዝምታን መርጦ የተቀመጠውን ተገፊ በማይመጣ መንገድ መጥተው ነካኩት ። ከቀያቸው ከወልቃይት ተገፍተው ጎንደር የከተሙትን የወልቃይት ኮሚቴዎች ለመጥለፍ በተደረገው ትልቅ ስህተት / መታበይ / ለክብሩ ሟቹን አማራ ከጫፍ እስከጫፍ በቁጣ አስነሱት ። ያ ሆነና የተኛውን ” ኢትዮጵያዊ አንበሳ ” ቀስቅሰው ካስነሱት ወዲህ ነገሮች ተቀያይረዋል ! አማራ ከጫፍ እስከ ጫፍ ተቆጥቷል ! በሰፊው ስንሰማ እና መረጃዎችን ስናይ በእርስ ግጭቱና የጥፋት አዙሪቱ እንዳንገባ እንሰጋለን ! የህዝብ ቁጣ ዳግም እንዳይገነፍል ስጋቱ አይሎ ባለበት በዚህ ሰዓት ህዝቡ ከመንግሰት በልጦ መገኘቱ ደግሞ በጅቶናል ፤ በአፄ ፋሲል ውቅር ከተማ ፤ በብልህና የዋሁ ቅን መሪ በጻዲቁ ዮሃንስ ብሩክ ምድር ፤ በሃገር ወዳዱ የአፄ ቴዎድሮስ እንዲህም ሆኖ ሰንብቷል !

ዛሬ በሚከወነው ህዝቡ በራሱ የጠራውን ተቃውሞ የስራ ማቆም አድማን ጥሰው ስራ የጀመሩ አንድ ባጃጅ መቃጠሉንና የተወሰኑ ሚኒባሶች መስታዎት መሰበሩን ከነዋሪዎች ለማረጋገጥ ችያለሁ ። በሌላ በኩል ለሶስት ቀናት የጎንደር ከተማ የመንግስት መ/ቤትና የግል ድርጅቶች እንቅስቃሴ ተገትቶ እንደነበር አንድ የአማራ ክልል ቁልፍ ቦታ የሚሰሩ ወዳጄም አልደበቁኝም ! “ ተጠሪ የሌለውም ” ያሉኝ አድማ በበራሪ ወረቀት መጠራቱን አምነው በተሽከርካሪዎች የደረሰውን ጥቃት አስተባብለውታል ። እሳቸው“ ተጠሪ የለውም” ቢሉም ሀገሬው “ ጠሪ ከዋኞቹ እኛው ነን !” እያለ የተጠራነው አድማ ለሶስት ቀን ተደርጎ ዛሬ ይከዎናል ! እነሆ ነገም መልስ እስካልተገኘ ተቃውሞው የሚበርድ አይመስልም ። ከአደባባይ ሰልፍ ወደ ደም የማይገበርነት በዘመነ የህዝብ የቀረበውን ጥያቄ መመለስና ለተገደሉት ፍትህ መስጠት ፡ በጀምላና በግፍ የታሰሩትና የሚሰቃዩትን ወጣቶች መፍታት ብቸኛው አማራጭ መሆኑን ነዋሪው እየተናገረ ነው ፤ ይህ ካልሆነ ነገም ቀዝቀዝ ብሎ በሚግመው የህዝብ እንቢተኝነት ማሳያ ተቃውሞ መዳረሻው የት ሊሆን እንደሚችል መገመት አይቻለንም !

ቸር ያሰማን ! 、

ነቢዩ ሲራክ
ነሐሴ 10 ቀን 2008 ዓም

Viewing all 15006 articles
Browse latest View live