ከአየነዉ ብርሃኑ
ዉድ አንባቢያን የመጣጥፏ መነሻ ሃሳብ የተወሰደዉ ”The Battle of Adwa, African victory in the age og Empire በሚል ከ Raymond Jonas በ 2011 ክተጻፈ መጽሃፍ መሆኑ እንዲታውቅልኝ አሳስባለሁ ።
አገራችን ኢትዮጵያ ትልቅ አገር ነበረች፡ ህዝቧም ለዕምነቱ ያደረ፤ስብእናን የተላበሰና ለእዉነትም ሟች እንድነበረ ከዕድሜ ጠገብ ሊቃዉንት እና ከቅሬተ መረጃዎቻችን መረዳት ይቻላል።
አያሌ አገራት ከኢትዮጵያ በኋላ እየተነሱ ዛሬ ገናናዎች ሆነዋል በአንጻሩ ግን የኛ ኢትዮጵያ እንደ አገር ኢትጵያዉያንም እንደ ህዝብ የመጨረሻ ዉዳቂዎች ሆነን ዓለም ተጠይፎናል ።ይህ ሁሉ ርካሽነት ከምን መጣ፟ ?
በኢትዮጵያዉያን ዘንድ ስብእናን ማዋረድ፤ ለእዉነት ከመቆም ይልቅ ሃሰትን መድፈር፤ ከጋራ ጥቅም ይልቅ ለግል ጥቅም መገዛት በአጠቃላይም ለኢትዮጵያዊነት እሴት እየተሟጠጠ መሄድ ምክንያቱ የዉጭ ወራሪ ሃይላት ኢትዮጵያ ዉስጥ መግባት መጀመር ሲሆን ይህ ክስተት ይበልጥ መልክ እየያዘና እየተጠናከረ የመጣዉ ግን በጣሊያን ወረራ ነዉ ይላሉ ጠበብት።
ጣሊያን ኢትዮጵያን ለመዉረር ሲያቅድ መጀመሪያ ላይ ዕግሩን ያሳረፈዉ ምጽዋ ላይ ነዉ። ከምጽዋ ወደ መሃል አገርና ወደ ደጋዉ ለመዝለቅ ግን ለጣሊያን ቀላል አልነበረም።
ዶጋሊ ላይ በራስ አሉላ መሪነት በተደረገዉ ጦርነት ወሬ ነጋሪ እንኳን ሳይቀር የጣሊያን ጦር ድምጥማጡ እንዲጠፋ በመደረጉ የጣሊያን ወይዛዝርት ከል እንዲለብሱ ፖለቲከኞች ወደ ህዝብ ፊት ለመቅረብ ሃይል ያጡበት እና የወታደር ሃላፊዎች ለማመን የሚያቅት ሽንፈት እንዲቀበሉ የተገደዱበት ሁኔታ ተፈጠረ። በጣሊያን ምድር ዋይታዉ ቀለጠ እናም እንደ ማጽናኛ ተደርጎ የተወሰደዉ ለአለቁት ጣሊያኖች ሃዉልት ማሠራት እና ሃይልን አጠናክሮ ወደ ኢትዮጵያ መመለስ ሆነ።
ጣልያን ሃይሉን አጠናክሮ ወደ ኢትዮጵያ ቢመለስም ኢትዮጵያዉያንን ፊት ለፊት መግጠም ግን አሁንም የሚሞከር አልሆነም እና ሌሎች መንገዶችን ማፈላለግ ነበረበት። ጠቃሚ ነዉ ተብሎ የታመነበትም መንገድ ለጣሊያን ያደሩ ኢትዮጵያዉያንን በመመልመል በግንባር ማሰለፍ የሚል ሆነ።በዚህም መሠረት በህብረተሰቡ ዉስጥ ችግር ያለባቸዉን ግለሰቦች ለምሳሌ ሌቦችን ፤ ቀጣፊዎችን እና በአጠቃላይ በህብረተሰቡ ዘንድ ተቀባይነት የሌላቸዉ ግለሰቦችን በመመልመል የተጀመረዉ የባንዳ ምልመላ በአጭር ጊዜ ዉስጥ አድጎ ጣሊያን አያሌ የአስካሪስ ወይም ባንዳ ባታሊዮኖች ለማቋቋም ቻለ።
ጣሊያን ይህንን ሲያደርግ ለአጭር ጊዜ ድል ብች ሳይሆን ለረጅም ጊዜ ዕቅዱ በሚያመቸዉ መንገድ ነበር። በዚህም አንድ ባንዳ ወታደር ሲቀጠር ሚስት እንዲያገባ እና ቤተሰብ እንዲመሠርት የቤተሰቡ አባላትም በወታደራዊዉ ስራ እንዲሳተፉ ከማድረግ ባሻገር የጣሊያንን ቋንቋ ባህል እና አጠቅላይ ከኢትዮጵያዉያን የሚለዩበትን መንገድ እንዲያጠናክሩ ከፍተኛ ጥረት ይደረግ ነበር ይላሉ ጸሃፍት። ይህ መሆኑ ነዉ እንግዲህ የባንዳነት መሠረቱ።
አስካሪም ይበለዉ ባንዳ ወይም ባሺ ቡዙቅ የቅጥረኛ ጥርቅም ጊዜዉ ይዘግይ እንጂ ጣሊያንን ከዉድቀት ሊያድነው አልቻለም እና ጣልያን ከመሸነፍ አልዳነም።እንዳልሆነም ሆኖ ወደመጣበት ተመልሶአል ። ጥሎት የሄደዉ ጠባሳ ግን ይሀዉ አንድ ምዕተ ዓመት ሙሉ እያመሰን እያተራመሰን እና ህልዉናቺንንም እየተፈታተነን ነዉ።
ይህ ወገንን በወገን ላይ ማነሳሳት እና እርስ በእርስ ማናከስ ስልጣንን ለማስፋፋት እና የሥልጣን እድሜንም ለማራዘም ተመራጭ መንገድ ሆኖ በመገኘቱ ከጣሊያን መባረር በኋላ በተከታታይ የተነሱ መንግሥታትም ይሁን ብለዉ ተቀብለዉ በሥራ ላይ አዉለዉታል።
የፊዉዳሉ ሥረአት ቁንጮ የነበሩት ንጉስ ወደ መንበረ ሥልጣናቸዉ ሲመለሱና መንግሥታቸዉን ሲያዋቅሩ ቅድሚያ የሰጡት ለጣልያን አገልጋይ ባንዶች ሲሆን ጣሊያንን አስጨንቀዉ ላባረሩ አርበኞች ግን መጨረሻቸዉ ስቅላት ግዞትና እንግልት እንደነበር ከታርክ ብቻ ሳይሆን ከኣይን ምስክሮች የምነሰማዉ ሃቅ ነው።
መንግሥታቸዉንም ካዋቀሩ በኋላ ቢሆን የንጉሱ የትኩረት አቅጣጫ አድርገዉ የወሰዱት ህዝብን ረግጦ መያዝ ነበርና ጀሮ ጠቢ በሚል የሥለላ መረብ በመዘርጋት ለሀገሩ እና ለወገኑ የሚያስብ ዜጋ እድሜ እንዳይኖረዉ የተቻለዉ ሁሉ ሲደረግ ቆይቶአል።
ከዚህም ባሻገር ለጣሊያን ለማደር የመጀመሪያዉን ደረጃ ለያዘዉ ለሰሜኑ ክፍል ቅድሚያ በመስጠት በትምህርት በልማት እና በመሳሰሉት ጥቅማ ጥቅሞች የአገር ሀብት ያላግባብ እንዲባክን አድርጎአል የፊዉዳሉ ሥረኣት።
የህረተሰብ የንቃተ ህሊና ዕድገት እና ለዉጥ ፈላጊነት የታሪክ ሂደት ነዉ ። በመሆኑም የብሶት መጠራቀም የፊዉዳሉ ሥረአት ከነግሳንግሱ እንዲገረሰስ አድርጎታል።
በፊዉዳሉ ሥረዓት እግር የተተካዉ ወታደራዊዉ ሥረኣትም ቢሆን የመጀመሪያ ዓላማዉ አድርጎ የተነሳዉ የሥልጣኑን መሠረት ማደላደል ነበር እና ይህንንም ለማድረግ ይሆኑኛል የሚላቸዉን የህብረተስብ ክፍሎች ከጎኑ ለማሰለፍ ጊዜ አልወሰደበትም። ለደርግ ያደሩ ምሁራንም የአቅማቸዉን ሞከሩ በህዝብ ግድያ ላይ የተሰማሩ ነፈሰ ገዳዮችም እጃቸዉ በደም ቢጨቀይም የህዝብ እምቢተኝነት እያደገ በመምጣቱ ሥልጣን ማደላደሉ ለደርግ አልጋ በአልጋ አልሆነም።ትግሉም ቀላል የማይባል የትዉልድ ጥፋት አስከትሎአል። በወታደርዊ መንግሥትና በለዉጥ ፈላጊዉ ኢትዮጵያዊ መካከል በተደርገዉ ፍትጊያ አንድ ትዉልድ አለቀ። የዚህ ፍትጊያ ጠባሳ ዛሬ አገራችን በአስካሪስ ዉላጆች እጅ ወድቃ እንዳልሆነች እንድትሆን እና ህዝቧም አዉራዉን እንድተነጠቀ ንብ ባዝኖ እንዲቀር ለማድረግ የራሱ አስተዋጸኦ አድርጎአል።
የፊዉዳሉ ሥረኣትም ሆነ የወታደራዊዉ ሥረኣት እንደነበሩበት የዕድገት ደረጃና የህብረተሰቡ የንቃተ ህሊና ደረጃ የጭቆናዉ ደረጃ ቢለያይም በጠንካራ ጎን በኩል አንድ የሚያደርጋቸዉ ዓቢይ ጉዳይ እንደነበር ግን አሌ የማይባል ሃቅ ነዉ ። በአገር እንድነት እና በብሄራዊ ስሜት በኩል በማይናወጥ መሠረት ላይ የተመሠረተ ዕምነት ነበራቸዉ።የኢትዮጵያንም ህዝብ በእኩልነት የማየት ባህሪ ነበራቸዉ። ህዝብ ከህዝብ የሚስማማበትን እንጂ ህዝብ ከህዝብ የሚናቆርበትን መንገድ ሲያሰሉ ዉለዉ አያድሩም ነበር። የፖለቲካ እንጂ ሁለቱም ሥረኣቶች የዘር ጠላት አልነበራቸዉም።
ለትግራይ መገንጥልና የዮሃንስን ሥርዎ መንግስት ለማስመለስ ወደ ጫካ የገቡት የዛሬዎችቹ የኢትዮጵያ ገዢዎች በለስ ቀንቶአቸዉ ሠፊዋን ኢትዮጵያ ለመቆጣጠር ቻሉ።የኢትዮጵያ ህዝብ የደርግን አስከፊነት አሻግሮ ሲያይ በሩን ለነዚህ ማሺንኮች ወለል አድርጎ ከፈተላቸዉ።እነሱም እግራቸዉን ካስገቡ በኋላ መሠሪ ተግባራቸዉን ቀጠሉበት።
በጣሊያን የተጀመረዉን በዘር የመከፋፈል ተንኮል እና በፊዉዳሉ ሥረአት እና በወታደራዊዉ አገዛዝ የነበረዉን አገልጋይን የማብዛት ዘይቤ አሻሽለዉ ቀጠሉበት። የፊዉዳሉ ሥረኣትም ሆነ ደረግ ባንዳን የሚመለምሉት በግልሰብ ደረጃ ነበር። እነዚህ ዘረኞች ግን ድርጅታዊ መልክ ሰጡት። በዚህም የአገሪቱን ህዝቦች በዘር ከፋፈሏቸዉ ። ባንዳነትንም አስከፊ ገጽታ አላበሱት።
አናሳዎች ናቸዉ። አገር የመምራት ራዕይ የላቸዉም። እዉቀቱም ያንሳቸዋል። ህዝብን እያጠፉ እንጂ እያለሙ የመምጣቱ ልምዱ የላቸዉም። በመሆኑም ኢትዮጵያን እየገዛን እንቀጥላለን የሚለዉ ድፍረቱ የላቸዉም። መጀመሪያዉንም ሳያስቡትና ሳያልሙት የመጣ ወርቃማ አጋጣሚ በመሆኑ እንጂ !! ከዚህም የተለየ ሊያደርጉ አይችሉም።
የሥልጣናቸዉም መቆናጠጫ የመጀመሪያዉ አድርገዉ የወሰዱት ድርጅታዊ መልክ ያለዉ የባንዳ መልመላ ነበር ። ለዚህም ነው ከጦር ምርኮኞች ዉስጥ እምነት ያሳደሩባቸዉን እና ወዶ ገብ የኢህአፓ አባላትን በማሰባሰብ መድረሻዉን እና ዓላማዉን ያላዎቁትን ኢህድንን እንደ አገራዊ ድርጅት ኦህዴድን ለኦሮም ህዝብ በኋላም ደህዴንን ለደቡብ ህዝቦች ጠፍጥፎ በመሥራት ለሥልጣን መቆናጠጫ መንገዳቸዉን አመቻቹ። ዘረኞቹ አራት ኪሎን ሲቆጣጠሩ ዛሬ ያሉበት የማይታወቅ ያኔ ግን እንደ አሸን ፈልተዉ የነበሩት እኛም ተበድለናል ባይ ግለሰቦችና ድርጅቶች ከዘረኞች ጎን ተሰለፉ በዚህም አናሳዎቹ የልብ ልብ ተሰማቸዉና ጫካ ዉስጥ የጻፉትን ታሪክ መምዘዝ ጀመሩ የኢትዮጵያም ታሪክ መቶ ዓመት ብቻ እንደሆነ ተለፈፈ።ምኒልክ ትምህርት ቤትም ሆነ መንገድ ያሠራ የነበረዉ ለወረራዉ እንዲያምቸዉ እንጂ ለኦሮም ህዝብ መማሰብ አልነበረም የሚለዉ ሠበካ በደደቢት ካድሪዎች ብቻ ሳይሆን ለዚሁ ተግባር በጥንቃቄ በተመለመሉ ባንዳዎች እንዲስተጋባ ተደረገ ።… እና ሠገራ እያደር ይገማል ፤ ትግሬና ቆርቆሮ ሳይነኩት ይጮሃል እየተባልክ ኖረሃል ዛሬ ጊዜዉ ያንተ ነዉ የሚሉት እና የመሣሰሉት ህዝብን ከህዝብ የሚያጫርሱ አደገኛ ቅስቀሳዎች በአዳራሽ ዉስጥ ስብሰባ መስበክ ተጀመረ ። በርግጥ ግን ለዚህ መርዘኛ ቅስቀሳ ሰለባ የሆነ የህብረተሰብ ቁጥር ምን ያህል እንደሆነ ጊዜ የሚፈታዉ እንቆቅልሽ ሆኖ ይቆያል ።
ዋናዉ የዚህ ጽሁፍ ትኩረት የትግራይ ዘረኞች ቢቻል ኢትዮጵያን እስከ ወዲያኛዉ በመግዛት ካልሆነም የአገሪቱን ሃብቷን በመዝረፍና ህዝቧን በማጎሳቆል ኢትዮጵያ የምትባል አገር ደግማ እንዳታንሰራራ ማድረግ ባንጻሩ ግን በሃብት የበለጸገች ፤ በፋብሪካ ላይ ፋብሪካ የገነባች የምእራብ እና ደቡብ ምእራብ ኢትዮጵያን ያጠቃለለች ለም እና ታላቋን ትግራይ መመሥረት መሆኑ ባለፉት 25 ዓመታት ያከናዎኑት እና አሁንም እየገፉበት ያለዉ ተግባር መሆኑ ጸሃይ የሞቀዉ ሀቅ ሆኖ ሳለ በታሪክ ሠሪነቱ ከማንኛዉም በኢትዮጵያ ዉስጥ ከሚኖር የህረተሰብ ክፍሎች የበለጠ እንጂ ያነሰ ድርሻ የሌለዉ መሆኑ የሚታወቀዉ ፤ በጸረ ኮሎኒያል ተጋድሎ ከማንም የበለጠ ተጋድሎ መስዋዕትነት የከፈለ ህዝብና ዕዉነትኛ ማንነቱን እና የአገር ባለቤትነቱን ሃቅ ለማስጨበጥ የምሁራን ችግር አለበት ተብሎ የማይታማዉ የኦሮሞ ህዝብ እንዴት ለነዚህ መሠረተ ባንዳዎች ጠባብ ፕሮፓጋንዳ ሠለባ ሊሆን ቻለ ?
የኦሮሞ ህዝብ በጦር ሜዳ ምርኮኞች ለተመሠረቱዉ ኦህዴድ ብዙም ቁብ እንዳልሠጠዉ በኣንጻሩ ግን ዕምነቱም ተስፋዉም የኦሮሞ ነጻነት ግምባር እንደነበር ሌላዉ ቀርቶ ራሳቸዉ የወቅቱ የሥልጣን ባለቤት የሆኑት ዘረኞች የማይክዱት ሀቅ ነዉ።
የኦሮሞ ነጻነት ግምባር ምሁራን መጀመሪያ ላይ ከወያኔ ጋር መጎዳኘታቸዉ ይሁን እሺ መሰላቸዉ እንበል ። ከሻቢያም ሆነ ከወያኔ መሪዎች ጋር በነበራቸዉ ወዳጅነትና በቋመጡለት የሥልጣን ፍላጎት ያልሆነዉን ሆነ ብለዉ ተቀበሉት እንበል። ወያኔም ሆነ ሻቢያ በስልጣን ላይ ናቸዉ። የኦሮሞ ፖለቲከኞች ግን ዛሬ እንኳን አገር ሊመሩና ህዝብ ሊያስተዳድሩ ይቅርና ለራሳቸዉም መሆን ቸግⶂቸዉ ሰባት ቦታ ተበታትነዉ ለገላጋይ ባስቸገሩበት ደረጃ ላይ ደርሰዋል።ወድቀት ኣዲስ ነገር አይደለም ክፋቱ ከዉድቀት ተምሮ መነሳት አለመቻል እንጂ።
ይህን ስል የኦሮሞ ምሁራንን ለማስቀየም በማሰብ እንዳልሆነ ይታወቅልኝ ይህን ጀግና ህዝብ ከታሪክና ከሀገር ባለቤትለቱ ለመነጠል የተኼደዉ እቀት እያሳዘነኝ እንጂ !!
በእርግጥ ለሩብ መዕተ ዓመት ያህል በአገር ላይ በደል በህዝብ ላይም ሞልቶ እየፈሰሰ ያለ ግፍ ተፈጽሞአል። ህዝብ ማንነቱን ካጣ ቆየ ሃብቱም ተመዘበረ በእነዚህ በልተዉ በማይጠግቡ አግኝተዉ በማይረኩ አሸንፈዉ በማያዉቁ ህዝብን በማዋረድ ብቻ በሥልጣን ላይ እንቆያለን ብለዉ አልመዉ እየተንቀሳቀሱ ባሉ ጉዶች በዓለም ላይ ያልታዩ አገራዊ በደሎች እየተፈጸሙ ነው። እያወቁም ይሁን ሳያዉቁ የኦሮሞ ፖለቲከኞች ለዚህ ሁሉ ግፍ አስተዋጸኦ አድርገዋል።
ቢዘገይም አሁን ግን ወደ ሃቅ መመለሻዉ ላይ ያለን ይመስለኛል እነዚህ ጉዶች በቃችሁ የሚባሉበት ወቅት ላይ ደርሰናል የማይናወጥ የህዝብ አቋም!!
አንድ አንድ ብልጣ ብልጥ የኦሮሙ ምሁራን ታሪኩን በማዛባት በሃቁ ላይ ሳይሆን በእነሱ ፍላጎት ላይ የተመሠረተ ታሪክ ለመጻፍ እንደሞከሩት ሳይሆን የኦሮሞ ህዝብ በዛሬይቱ እትዮጵያ ምሥረታ ላይ የጎላ አስተዋጸኦ አድርጎአል። ለኢትዮጵያ ነጻነት ከማንም በላይ ተጋድሎ ያደረገ ደሙንም ያፈሰሰ ጀግና ህዝብ ነዉ።
ይህንንም የኦሮሞ ህዝብ ጀግንነት ዮናስ በመጽሃፉ ምዕራፍ 14 ላይ ፍርሃት ሽብርና ተስፋ መቁረጥ በሚለዉ ርዕስ ሥር እንዲህ ሲል ይገልጸዋል፤
”ምኒልክ አድዋ ላይ ድል ሲቀዳጅ የተጻፈ ህግ አልነበረዉም። ወታደሮቹ አልሰለጠኑም ።ወታደራዊ ሙያም አልነበራቸዉም። ክፍያም አልነበራቸዉም። በአዋጅ የተሰባሰቡ ነበሩ። በወኔና ብኄራዊ ስሜት ተሞልተዉ መሣሪያ ያነሱ ዜጎች ነበሩ።ከቅርብ አለቆቻቸዉም ሆነ ከንጉሳቸዉ እንዲሰጣቸዉ ከሚጠብቁት መሣሪያና ከሚጠብቁት ሹመት በስተቀር ምንም ነገር አልነበራቸዉም።
ጦርነቱ ጠንክሮ ከመደበኛ ጦርነት ወደ ጨበጣ ዉጊያ ሲሸጋገር የኢትዮጵያ ወታደሮች ድል የማድረግና የመዝናናት ስሜት አልታየባቸዉም።ሃይላቸዉን በማጠናከር የጣሊያንን ወታደሮች ማባረሩን ተያያዙት እንጅ።የጣሊያን ወታደሮችም ሲሸሹ ማየት የኢትዮጵያን ወታደሮች ወኔ ከፍ አደረገዉ።በአንጻሩ የጣሊያን ወታደሮች የወደፊት እጣ ፋንታቸዉ መቁሰል መሞት እና ያላቸዉን ሁሉ ማጣት መሆኑን ቀድመዉ ስለተረዱት የሞራል ዉድቀት ደረሰባቸዉ ይህም ዉድቀታቸዉን አፋጠነው።” ይልና በመቀጠልም መበታተን እና ሺሺት በሚለዉ ርዕስ ስር ይቀጥላል፤
”አልቤርቶኒ ከብዙ አዋጊ መኮንኖቹ ጋር ከተማረከ በኋላ በእርሱ የተመራዉ ብርጌድ ፍርስርሱ ወጣ።ወታደሮቹም በተበታተነ መልኩ ሺሺት ጀመሩ።አልቤርቶኒ ከመያዙ በፊት ወታደሮቹን ለማሰባሰብ እና ለማደራጀት ሞከረ ግን አልተሳካለትም ምክንያቱም የመጀመሪያዎⶩ ሽሽት ጀመሪዎች ለጣሊያን ያደሩ ባንዶች ስለነበሩና ከአባራሪ የኢትዮጵያ አርበኞች ለመለየት አልተቻለምና። ከዋናዉ የጣሊያን ጦር ሠፈር ዳቦር ሜዳ የሚያገናኘዉ መስመር በኢትዮጵያ አርበኞች ተዘጋ። አባራሪና ተባራሪ ተቀላቀለ በጣሊያን ወታደሮች መካከልም መደናገር ተፈጠረ።ከፊታቸዉ እየተመመ ያለዉን የጦር ማዕበል ሲመለከቱ እነ አሪሞንዲና ሌሎችም የጣሊያን ጦር አዛዦች ግራ ገባቸዉ ። በአንጻሩ የኢትዮጵያ አርበኞች መተላለፊያ መንገዶችን በመዝጋት የሚሸሹትንም ወታደሮች በማሳደድ ከጦር መሪዎች ጋር በቅርብ ርቀት የጦርና ጋሻ መሞሻለቅ ሲጀምሩ የጣሊያን ጦር ተፈታ።በጁሴፔ ባዉዲኒ የሚመራዉ ባታሊዮንም ቢሆን ለዝግጀት ጊዜ አላገኘም። በኢትዮጵያ አርበኞች ተከበበና ተማረከ።ጀኔራል ባራቴሪ ያገሩን ባንዲራ እያዉለበለ በአገሩ ነገሥታት ሥም ቢማጸንም በሺሺት ላይ ያለዉን ወታደር ማስቆም አልቻለም።ሰሚ አላገኘም።ሁሉም እግሬ አዉጭኝ ወደ ኤርትራ ሆነ።በመጨረሻም ባራቴሪ ራሱ በቅሎዉን መጭ በማለት ሺሺቱን ቀጠለ።በሺሺት ላይም እንዳለ መነጸሩ ወደቀበት ለማንሳትም ጊዜ አላገኘም።ሌላኛዉ ጀኔራል እንደ ዓይን እያገለገለዉ ትዕዛዝ ለማስተላለፍ ቢሞክርም ባራቴሪ የሠራዊቱን ሽሽት ለማቆም አልቻለም።
ጭንቀት ፍርሃት እና የመጨረሻዉ ዉድቀት አይቀሬነት በጣሊያን ወታደር መካከል በነገሠበት ወቅት የኦሮሞ ፈረሰኞች በቦታዉ ፈጥኖ መድረስ በጣሊያን ጦር ዉስጥ የነገሰዉን ጭንቀት አባባሰዉ። ዉድቀቱንም አፋጠነዉ።ኦሮሞዎች ፈረሰኞች ናቸዉ።ፈጥኖ በመድረስ፤ ቦታ በመያዝና ፈጥኖም ጥቃት በማድረስ ወደር አይገኝላቸዉም።
ይህ የኦሮሞዎች ጀግንነት ወደ አዉሮፓ ይዘግቡ በነበሩ የአዉሮፓ የዜና ማሠራጫዎች ተረጋግⶏአል።ከፈረሰኛነታቸዉ ባሻገር እጨደዉ \mow them down/ የሚለዉ የኦሮሞዎቹ አዝማች ቃል በጣሊያን ምድር መደመጡ የጣሊያን ሲቪሎች በመንግስታቸዉ ላይ ጥያቄ እንዲያነሱ ብቻ ሳይሆን ለዘመቻ የተዘጋጁ ተተኪ ወታደሮችም ጭንቀት ላይ እንዲወድቁ አድርጏል።” ይላል ዮናስ በመጽሃፉ በመቀጠልም፤ ”ጣሊያኖች ፈረስ የላቸዉም ፈረስ መጋለብም አይችሉም።የነበራቸዉ አማራጭ መሣሪያን እየጣሉ መሸሽ ብቻ ነበር።የጣሊያን ጦር ሺሺት ለኦሮሞዎች ምቹ ሁኔታን ፈጠረላቸዉ።በራሳቸዉ ላይ የደፉት የአንበሳ ጎፈር ኦሮሞ የሚለዉን ስማቸዉን አጎላዉ።ጀግና ተዋጊነታቸዉን እና አስፈሪነታቸዉንም ጨመረዉ።ይህም የኦሮሞዎች አስፈሪነት የጣሊያን ጦር ሞራል እንዲንኮታኮት ጉልህ ሚና ተጫዉⶆል።የኦሮሞዎች አስፈሪ ተዋጊነት እና ኦሮሞዎች መሳሪያ ይዞ ያገኙትን የጣሊያን ወታደር ይሰልባሉ castrate የሚለዉ ማስፈራሪያ ሁሉም የጣሊያን ወታደር መሣሪያዉን እየጣለ እንዲሸሽ አግⶋኣቸዋል።
አንድ የጣሊያን ወታደር ሸሽቶ ኤርትራ ብዉስጥ ከሚገኘዉ ካምፕ ሳዉራ ቢደርስም ህሊናዉን ግን ስቶ ነበር። በካምፕ አካባቢ በመዞርና ያልተለመደ ፈገግታ በማሳየት የኦሮሞ ፈረሰኞ አስፈሪዎች አስፈሪዎች እያለ ይጮህ ነበር።”
በማለት ነበር ዮናስ የኦሮሞን ጀግንነት የገለጸዉ። በዚህ ብቻ አላበቃም እንዲ ሲል ይቀጥላል፤ ”በጀኔራል አርሞንዲ ስር የነበረ አንድ የጣሊያን ጦር የበታች አዛዥ ኦሮሞዎች በጦርነቱ ላይ የነበራቸዉን ወሳኝ ሚና እንዲህ ሲል በሚገባ ገልጾታል።”ወደ ይዞታችን እየተመመ የሚመጣዉን የኢትዮጵያን ወታደር ስመለከት ወደ ስምጥ ሸለቆ የሚፈስ የባህር ማዕበል ይመስል ነበር ብሎታል”።በዚህም ብርጌዱ በኦሮሞ ጦር ተከበበ ጣሊያኖችም ለመከላከል ሞከሩ።ከመራር ጦርነት በኋላ ግን የሰው ሃይላቸዉ እየተመናመነ መሣሪያቸዉም እያለቀ በመሄዱ በጣሊያን ጦር አዛዦች መካከል ፍርሃትና ጭንቀት ነገሠ።መሸሽ በራሱ የማይቻልና ከጦርነት የበለጠ አስፈሪ ሆነ።በኦሮሞ ተዋጊዎች ከመማረክ ራስን ማጥፋት የተሻለዉ አማራጭ ሆኖ ተገኘ። በመሆኑም የጣሊያን የጦር አዝማቾች አንዱ ከሌላዉ በፊት ራሱን ለማጥፋት መሽቀዳደሙን ተያያዙት።ጀኔራል ጋሪባልዲ የሁሉም ፍጻሜ መሆኑን በመረዳት ሞትን መረጠ።
ያለ መልዕክትም ይኸዉ ነዉና ጥሪዉ አፋጣን ምላሽ ይጠይቃል።
ያገሪቱ ምሁራን ችግር የመፍጠር እንጂ ቺግር የመፍታት ልምዱ ባይኖራቸዉም ከዘመኑ ትዉልድ ትምህርት ይዉሰዱ ። እናም አብሮነት ይሰበክ ፡ እነዚህን የትዉልድ አሽክላዎች ጠራርጎ ወደ አስቀያሚዉ የአገራችን የታሪክ ቅርጫት ለመጨመር ትግሉ ይፋፋም። ታሪክ ለባለ ታሪኩ አገርም ለባለ ኣገሩ ነዉና!!!
እግዚአብሔር እትዮጵያን ይባርክ
ህዝቧንም መንፈሰ ጠንካራ ያድርግ !!