Quantcast
Channel: Ethiopian News | ዘ-ሐበሻ | Latest News Provider | News For All
Viewing all 15006 articles
Browse latest View live

ድምፃዊ ማዲንጎ አፈወርቅ የኢትዮጵያን ሕዝብ ይቅርታ ጠየቀ |“አምኜበት ደስ እያለኝ ነው ይቅርታ የጠየቅኩት”

$
0
0


(ዘ-ሐበሻ) አርቲስት ማዲንጎ አፈወርቅ የኢትዮጵያ ሕዝብ ይቅርታ እንዲያደርግለት ጠየቀ:: አርቲስቱ በኢሳት ራድዮ ከጋዜጠኛ ተቦርነህ በየነ ጋር ባደረገው ቃለምልልስ “አምኜበት ደስ ብሎኝ ነው የኢትዮጵያ ሕዝብ ይቅርታ እንዲያደርግልኝ” ሲል ጠይቋል::

አርቲስቱ “ሕዝብን ይቅርታ ማለት ያንሳል:: ማንም አርቲስት ከሕዝብ ውጭ መሆን አይችልም::አልበሜንም ሰርቼ የገዛኝ እና ያደመጠኝ ሕዝብ ነው:: አርቲስት ከሕዝብ ውጭ መሆን አይችልም; ስለዚህ አምኜበት ደስ እያለኝ ነው ይቅርታ የጠየቅኩት” ይላል::

አርቲስት ማዲንጎ አፈወርቅ በተለይም በሰሜን አሜሪካ ያለውን ኢትዮጵያዊ ለሁለት ለመክፈል የሕወሓት መንግስት ቀንደኛ ደጋፊ የሆኑት ሼህ መሐመድ አላሙዲ የመሰረቱት ፌዴሬሽን ባዘጋጀው የመጀመሪያው ኮንሰርት ላይ በመሳተፍ የኢትዮጵያን ሕዝብ አስከፍቶ ነበር:: በዚህም በርካታ ኢትዮጵያውያውያን ቦይኮት ጠርተውበት እንደነበር አይዘነጋም:: ሆኖም ግን ማዲንጎ ከአንደኛው ዝግጅት በኋላ የአላሙዲ እግር ኳስ በዴንቨርም ሆነ አሁን ዘንድሮ በዋሽንግተን ዲሲ ሲደረግና በርካታ ገንዘብ እንደሚከፈለው ቃል ቢገባለትም እስካሁን ከሕዝብ ጋር የተቃቃርኩት ይበቃኛል በሚል እንደማይተባበር መግለጹና በኮንሰርቶቹ ላይ ሳይሳተፍ መቅረቱ አይዘነጋም::

ማዲንጎ የአንድነት ፓርቲ አመራርና አሁን በቅርብ ከ እስር ተፈቶ የውጭ ሃገር ህክምና ተከልክሎ የሚገኘውን ሃብታሙ አያሌውን ማንም አርቲስት ባላደረገው ሁኔታ ሃኪም ቤት ሄዶ በመጠየቅና ከ ሕመሙም እግዚአብሄር እንዲምረው በመመኘት ከሕዝብ ጎን መሆኑን አሳይቷል::

ማዲንጎ አፈወርቅ ሕዝብን በይፋ ይቅርታ የጠየቀበትና ሌሎች በርካታ ጉዳዮችን የሚያነሳበት ቃለምልልስ የፊታችን ቅዳሜ በኢሳት ራድዮ እንድሚቀርብ ጋዜጠኛ ተቦርነ በየነ አስታውቋል:: ይህን ቃለምልልስ ብዙዎች በጉጉት እንደሚጠብቁት አይጠረጠርም::

ማዲንጎ ሃብታሙ አያሌውን ሃኪም ቤት ሄዶ ከጠየቀ በኋላ በፌስቡክ ገጹ ያሰፈረው

ማዲንጎ ሃብታሙ አያሌውን ሃኪም ቤት ሄዶ ከጠየቀ በኋላ በፌስቡክ ገጹ ያሰፈረው


የአጋርነት መግለጫ ለጎንደር ሕዝብ እንቅስቃሴ –አገር ወዳድ ኢትዮጵያዊያን ከሎስ አንጅለስ እና አካባቢው

$
0
0

በ7/24/2016
amharaበሎስ አንጅለስ እና አካባቢዋ የምንኖር አገር ወዳድ ኢትዮጵያዊያን ተገናኝተን በአሁኑ ሰዓት በጎንደር የወልቃይት ሕዝብ የአማራ ማንነታቸውን በአግባቡ በመጠየቃቸው እየደረሰባቸው ስለአለው ስቃይ እና በሌሎችም አካባቢዎች እንዲሁ መሰረታዊ መብታቸው እንዲከበርላቸው ጥያቄ በማንሳታቸው እየደረሰባቸው ያለውን ኢሰብአዊ ድርጊት በሰፊው ተወያይተንበታል።

በተለይ በአሁኑ ሰዓት የወልቃይት ሕዝብ መሬቱን በግፍ ተቀምቶ የበይ ተመልካች መሆኑ ሳያንሰው የማንነቱ መግለጫ የሆነውን አማራነቱን በመካድ ያልሆነውን ነህ ተብሎ የተጫነበትን የማንነት ተፅእኖ በመቃወም በሚአደርገው የሞት የሽረት ትግል ይህ ጀግና ሕዝብ እያደረገልን ለአለው ጥሪ ዝምታን የሚመርጥ ህሊና ስለማይኖረን የምንችለውን ሁሉ ለማድረግ ቆርጠን ተነስተናል።

ከሰሜን እስከ ደቡብ፤ ከምስራቅ እስከ ምእራብ የኢትዮጵያ ሕዝብ ለመሰረታዊ መብቱ በመታገሉ ምክንያት እየደረሰበት ያለውን ማንኛውንም ኢሰብአዊ ድርጊት በጥብቅ እናወግዛለን። እየሞተ፣ እየተደበደበ፣እየታሰረ፣ ከቦታው እየተሰደደ እና ተዘርዝረው የማያልቁ ግፎች እየተፈጸሙበት  በእነዚህ ድርጊቶች ሳይበገር እየአደረገ ያለውን ተጋድሎ  ማድነቅ ብቻ ሳይሆን ለሚአደርገው ተጋድሎ አስተዋፅኦ ይኖራቸዋል ብለን የምናስባቸውን ሁሉ በየጊዜው እየተመካከርን ወደተግባራዊ እንቅስቃሴ ለመግባት ብሎም ተግባራዊ እንቅስቃሴ የሚአደርጉትን በማንኛውም መንገድ ለመርዳት ወስነናል።

በአገራችን ኢትዮጵያ በሁሉም አካባቢ እየተፈፀመ ያለው ግፍ የሚካሄደው በጭካኔው፣ ከባእድ የሱዳን ወታደሮች ጋር ወግኖ ወገኖቹን በማጥቃት፣በመካከላችን ያለውን ትስስር ለማላላት በማከፋፈል ስራው እና ለግድያ በአሰለጠነው አግአዚ በመመፃደቅ ሽብር በመፍጠር ተወዳዳሪ በሌለው የወያኔ ስርዓት ስለሆነ መፍትሄው ይህን ስርዓት ከስሩ ገርስሶ መጣል ብቻ መሆኑን ተረድቶ ሕዝቡ ትግሉን በሁሉም አቅጣጫ አቀጣጥሏል፡፡ እኛም በየቦታው የተነሳው  የፃነት ጥያቄ መልስ የሚአገኘው እና የዜጎች ደህንነት በአስተማማኝ ሁኔታ ተጠብቆ በሰላም መኖር የሚቻለው የሰላምና የአንድነት ጠንቅ የሆነው ስርዓት ሲወገድ ነው ብለን እናምናለን። በአንድ አካባቢ የሚፈፀመው አስከፊ ክስተት ነገ በሌላ አካባቢ የሚፊፀም እኩይ ተግባር ስለሆነ ይህንን ኃይሉን አሰባስቦ በተናጠል በሕዝብ ላይ ጉዳት እያስከተለ ያለውን ስርዓት ለማስወገድ የትግሉን አድማስ በማስፋት በሁሉም አቅጣጫ በአንድነት ስሜት ኃይሉን አሰባስቦ በጋራ እንዲነሳ ጥሪ እናስተላልፋለን። የሁላችንም ጠላት የሆነውን ወያኔ አስወግደን ሁላችንም ተጠቃሚ የምንሆንበትን ነፃነት ማግኘት የምንችለው አንድነት ኃይል መሆኑን ተረድተን በመቀራረብ በጋራ ስንሰራ ብቻ በመሆኑ ይህንን በመረዳት እየተቀራረቡ  ለመስራት ወስነናል።

 

ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ

 

ሞት ለወያኔ

አገር ወዳድ ኢትዮጵያዊያን ከሎስ አንጅለስ እና አካባቢው

ለወያኔ ህልውና ጠባቂዎች የቀረበ ጥሪ?   (“”ድሪባ ገመቹ””)

$
0
0

Woyane
ህዋሀት ወያኔ ሀርነት ትግራይ በኖረበት በሃያ አምስት አመታት በትግራይ ህዝብ ስም ለስርአቱ ቅርብ የሆኑ የትግራይ ተወላጆች ቱጃር ሆነዋል በርካታ ህንጻዎች ገብተዋል በተለያየ የሀገሪቱ ቁልፍ የንግድ ወይም በስልጣ እርከኖች ላይ ቆራጭ ፈላጭ ሆነው ተሠማርተዋል፣

በተቃራኒው ምንም  የሌለው የእለት ጉርስና ልጆቹን ወደ ትምህርት የሚልክበት የሌለው የትግራይ ተወላጆችም እንዳለ አይካድም, ነገር ግን እነዚህን የስርዓቱ ተጠቃሚ ያልሆኑ የትግራይ ተወላጆችን ወያኔ በተጨነቀበት ሠአት እየሠበሠበ ሠላማዊ ሰልፍ እያሥወጣ ፕሮባጋንዳ ሲሰራባቸው እና ከሌላው ኢትዮጵያዊያን ጋር እያጋጨ የራሡ የስልጣን ፍጆታ ማሟያ አድርጎ ተጠቅሞባቸዋል,
ሌላው ማህበረሰብም የትግራይ ህዝብ የስራዓቱ ተጠቃሚ ነው ወደሚል ድምዳሜ  እንዲደርስ አድርጎታል፣

አብዛሀኛው የትግራይ ተወላጅ የስርዓቱ ተጠቃሚ ባዮሆንም እንኳ ህውሀት ወያኔ ሀርነት ትግራይን ከመጥፎ ድርጊቱ እንዲታቀብ ሲቃዎም አይታዬም, በጣም በጣት የሚቆጠሩ ነገ የሚመጣውን አደጋ የተገነዘቡ ናቸው ህውሀት ወያኔ ልክ እንዳልሆነ እየተናገገሩ ያሉት፣
አብዛሀኛው የትግራይ ተወላጅ ግን ህውሀትን እንደ ፈጣሪው እየተመለከተ ህውሃት ስለሚበድለው ሌላኛው ህዝብ ዴንታ የሌለው መስሎ የሚታየው፣
ለምን ብለን ብንጠይቅ ወያኔ በትግራ ህዝብ ስም በርካታ ነገር ለመዝረፍ ይመቸው ዘንድ የውሸት ፕሮባጋንዳ ሲሰራበትና ህዝቡ ህዋሀትን አምኖ እንዲቀበል ለረጅም አመታት በትግራይ ህዝብ ላይ ሰርቶበታል፣

በአሁን ሠአት ለትግራይ ተወላጆች ጥያቄ የምናቀርብ እትዮጵያኖች ለትግራይ ተወላጅ በተደጋጋሚ ጥሪ እያስተላለፍን እንገኛለን?

ጥሪአችንም”
ህውሀት ወያኔ ሀርነት ግራይ የኢትዮጵያን ህዝብ ሲገድል ሲያስር ያለምንም ርህራሄ ቶርቸር ሲያደርግ ለስርአቱ ታማኝ ናቸው ያላቸውን በሀብት ሲያበለጥግ ኢሉንታ የሌለው የሹመት አሰጣጥ ሀገሪቱን በእውር ድንብ እንመራለን በማለት በበርካታ ችግሮች የተተበተበች ሀገር እንድትሆን አድርገዋታል, ይህንን ደግሞ መላው የኢትዮጵያ ህዝብ ሲመለከት ኖሯል,
ዛሬ ህዝቡ ትግስቱ ተሟጧል መብቱን ለማስከበር ቆርጦ ተነስቶአል።
የህዝብ ቁታ እንደማዕበል እየተጥለቀለቀ ለወያኔ አስደንጋጭ  ሆኖበታል፣ አንዳንድ የህውሀት የስርአት ታማኝ ተለላኪ በሆኑት ላይ ህዝብ እርምጃ እየወሰደ ይገኛል, በአሁን ሠዓት ህዝብ ዝምብዬ አልሞትም እየገደልኩ እሞታለሁ በማለት ከወያኔ ጋር እየተታኮሰ ይገኛል, ይሄ አሁን እያየን የለነው ጅምር ነው, ነገ በመላ ሀገሪቱ የህውሀት ተልእኮ አስፈጻሚ የሆናችሁ ኢላማ ታርጌት እንደምትሆኑ ከሠሞኑ የህብ ቂጣ መረዳት ትችላላችሁ, ለወያኔ የሚወረወረው  ጦር ሁሉ እናን ጋር እንደሚያርፍ ጥርጥር የለውም, ምክንያቱም አሁንም የወያኔ ተላላኪነታችሁን እስካላቆማችሁ ድረስ ህዝብ አፈሙዙን ወደ እናንተ ማዞሩ አይቀርም,
የህዝብን ቁጣ በምንም ታምር ወያኔ አያስጥልም።
ይህ ከመፈጠሩ በፊት ከአሁኑ ከተበደለው ህዝብ ጎን እንድትቆሙ እና ይህንን የህዝብ ትግል እንድትቀላቀሉ እንጠይቃለን ይህ ትግል እናንተንም ከወያኔ ባርነት ነጻ ለማውጣትም ጭምር መሆኑን መረዳት ይኖርባችኃል????

ህውሀት ወያኔ ሀርነት ትግራይ በሀገራችን ላይ ለሚፈጠረው ችግር ዴንታ የለውም, የትግራይ ህዝብ ከሌላው ህዝብ ጋር ቢጋጭም ለህውሀት ጉዳዬ አይደለም, ወያኔ ሁሌ የሚተጋው ለራሡ ህልውና እና ከሀገር ለዘረፈው ንብረት ብቻ ነው። ለህዝብ ዴንታ የሌለው እንደሆነ ደግሞ የሚያሳየው በትግራይ ህዝብ ስም ይሄንን ሁሉ በደል እየፈጸመ ነው የሚገኘው፣ ለዚህም ነው የትግራይ ተወላጆች ወያኔን ዞር በል በስማችን አትነግድ ብላችሁ ከሌላው ህዝብ ጎን ተሰለፉ ብለን ጥሪ እያቀረብን ያለነው?

ይሄ ትግል የመረረ ነው  በወያኔ ተገፍቶ ቆርጦ ለነጻነቱ የተነሳን ህዝብ ከዚህ በኃላ ማስቆም የማይቻል መሆኑን መረዳት ይኖርብናል, ከአሁኑ እራስን ለማዳን ሠልፍን ማስተካከል አስፈላጊ መሆኑን በአጽኖት እንመክራለን,,,,,???

ሠልፍ የጀግና ነው” ድል የእግዛብሔር ነው!!!!
እትዮጵያ ለዘላለም ትኑር,,,,,,,,,,,,,

የጎንደር ብርሃኖች –ከተማ ዋቅጅራ

$
0
0

13681020_626757367488618_5689809962206469958_n
በአለም አቀፍ ምልክቶች ሶስት ቀለሞችን አብዝተው ይጠቀማሉ አረንጓዴ ቢጫና ቀይ። አረንጓደው የመፍቀድ የይለፍ ምልክቶች ቢጫው የማስጠንቀቂያ ቀዩ ደግሞ የማገድ የማቆም ምልክት ሆነው በአለማችን በምልክትነት ይጠቀምባቸዋል። ኢትዮጵያን እነዚህን ቀለማቶች የአገር መለያ ሰንደቅ አላማ አድርጋ መጠቀም ከጀመረች ከአለም አገራት በፊት  ዘመናቶችን አስቆጥራለች አረንጓዴው የልምላሜ ቢጫው የተስፋ ቀዩ የጀግንነት ምልክት እንደሆነ ያመለክታል። ዛሬ ጎንደር ላይ ካረንጓዴው አልፎ ቢጫው በርቷል ባንድራዋንም ከፍ አድርገው አውለብልበዋል። አስተዋይ መንግስት ካለ የምጥ ጣር መጀመሪያውን ምልክት አሳይተዋል ቀዩ መብራት መብሪያው ግዜው ደርሷል። የዛን ግዜ ምክንያት አያድንም።

ለ25 አመት አማራ ተብሎ ሲገደል ሲሰደብ ሰወቀስ በሌላው ህብረተሰብ የማጥላላት ስራ ሲሰራበት የነበረ  ህዝብ ችሎ እና  ታግሶ ዝም ብው ተቀምጠው ነበር።  ይህ ማለት ኃይል ኖሮት እንደሌለው ጀግንነት ውስጡ ሆኖ እንደሌለው አሸናፊነት ባህሉ ሆኖ እንደተሸናፊነት ለ25 አመት ዝምታን መምረጡ አማራውን እና ኦርቶዶክስን ሃይማኖት አከርካሪውን ሰብረነዋል ብለው ተዛበቱበት። በነገራችን ላይ ኦርቶዶክስም እንደ ኦርቶዶክስ እንዲደራጅ ከተለያየ አካላት የተለያዩ  ጥቃት እና ትችት እየደረሰበት ነው። የኦርቶዶክስን ሃይማቶት በመስደብ እና በማንቋሸሽ የተሰማራችሁ መንግስታዊም ሆናቹ መንግስታዊ ያልሆናችሁ አካሎች ከድርጊታችሁ እንድትታቀቡ ከወዲሁ አሳስባለው በኋላ ልትከፍሉት የማትችሉትን ዋጋ ሊያስከፍላችሁ ይችላልና ጫናውና እርግጫው ከበዛ እንደ ኦርቶዶክስ እንዲደራጅ ታስገድዱታላችሁ ያኔ መቀልበሻው ሲለሚያጥር ከወዲሁ  ከድርጊታችሁ ብትቆጠቡ የሚለውን ትዕዛዛዊ መልእክቴን በዚሁ አጋጣሚ ማስተላለፍ  እፈልጋለው።

ጎንደር እና ኦሮሚያ ያረንጓደውን ግዜ ጨርሰው ቢጫው ላይ ነው ያሉት። አሁን የቢጫው መብራት በወያኔ ላይ በመላው ኢትዮጵያ እንደበራ እወቁ። ይሄ ቢጫ መብራት ወደ ቀዩ መብራት መሄዱ ግድ ነው። ቀዩ ከመብራቱ በፊት እና ሁሉም ነገር ከመፈጸሙ በፊት ቢጫው መብራቱ ሊያሳስብ ያለው ነገር አለ 1 መከላከያ ሰራዊት ቀይ ከመብራቱ በፊት የስርአቱ አገልጋይ ወይንስ የህዝብ? 2ኛ፡ከፍተኛ ባለስልጣናት ለወንበራችሁ ወይንስ ለህዝባቹ? 3ኛ፡ጋዜጠኞች ለሆዳችሁ ወይንስ ለህዝባቹ? 4ኛ፡ለሰላዮች ለጢቂቶች መኖር ወይንስ ለህዝብ መኖር? 5ኛ፡ለሃይማኖት አባቶች ለጨቋኞችን ማገልገል  ወይንስ የተገፋውን ህዝብን ማጽናናት? እንግዲህ ምርጫው የናንተ ነው ቀዩ ከበራ በኋላ ማለፍ የሌለባቸውን በሙሉ ይዞ ያስቀራል። ድል የህዝብ ነውና።

በኢቲቪ በፋና እና  ፌስ ቡክ ላይ በተሰማሩት የወያኔ አቀንቃኞች  እንዲሁም ስድብን ፣ ጥላቻን እና መለያየትን በመፍጠር የፖለቲካ እውቅናን ማግኘት ለሚሹ የፌስ ቡክ የስድብ አባቶች እና እናቶች ወደ ትክክለኘው መንገድ መምጣ ያለባችሁ ግዜ አሁን ነው። ጎንደር ላይ የተለኮሰው ኢትዮጵያን ያጠቃለለ ብርሃናዊ ህዝባዊ እንቅስቃሴ ቀድመው ለማዳከም  ቢሯሯጡም ቅሉ በያዙት ሚዲያም ወልቃይት የትግራይ ናት ለሚሉት ጠባቂ መከላከያ ተመድቦላቸው ሰልፍ እንዲወጡ ሲደረግ ወልቃይት የአማራ ናት ወገኖቻችንን በግፍ መግደል ይቁም ብለው ለሚወጡት ለጎንደር ህዝብ የተከለከለ ነው ተብሎ የማስፈራሪያ እና የዛቻ ቃሎችም ቢተላለፉበት ቅሉ የጎንደር ህዝብ ግን ቃሉን አክብሮ ዝምታውን ሰብሮ ቁጣውን ለመግለጽ እንደ 97ቱ  የአዲስ አበባ ሰልፍ መሬት አንቀጥቅጥ የህዝብ ሱናሚን በጎንደር ተደግሟል።

ከጎንደር ህዝብ በሰልፉ ግዜ የተላለፈው መልዕክት ኢትዮጵያዊ ወገኑን ሃይማኖት ከዘር ሳይለይ ያስተሳሰረ የወያኔን ጅማቶች የፈታ ሁሉንም ኢትዮጵያዊ በውስጥም በውጪም ያስደመመ ያወያየ  እና ለነጻነት በአንድነት ያነሳሳ ሰልፍ ነበረ።

ወያኔ ለ25 አመት ሲለፈልፍ ዝም ያለው ህዝብ ሞኝ እና ፈሪ የለፈለፈው ደግሞ ጀግና  እና ብልህ አድርጎ በያዘው ሚዲያ ቢያስነግርም በሰላም ዝም ብሎ የተቀመጠውን ህዝብ ነካክተው ነካክተው ጀግና  እና  ብልህ ማን እንደሆነ ይታያል ብሎ እሳት ሆነው ጎንደር ተነሳ ትግሉ ላይቀለበስ ወያኔዎች ኢትዮጵያን ለማነቅ ባዘጋጁት ሸምቀቆ እራሳቸውን ሊያንቃቸው የመጨረሻው ምዕራፍ ላይ ለመድረስ ወደ ቀዩ መብራት ጉዞ ተጀምሯል። በቅርብ ቀን በመላው ኢትዮጵያ ወያኔ ማለፍ ክልክል ነው የሚለው መብራት ፊታቸው ላይ ይበራል። ወያኔ  ስል ወያኔ ህውአትን ብቻ  ሳይሆን ወያኔአዊ ብአዴን ወያኔአዊ ኦፒዲኦ ወያኔአዊ ደህዴን ወያኔአዊ…. እያለ ይቀጥላል።

በጎንደር ህዝባዊ ሰልፍ ላይ የጀግኖች ሰልፍ ካሰኘው  በጥቂቱ ለመጥቀስ

  1. ህዝባዊ ሰልፉን ከማድረግ ምንም አያግደንም መትረየስ እንኳን ቢደገንብን ሰልፉን ከማድረግ የሚያስቆመን ምንም ሃይል አይኖርም
  2. መከላከያ ሰራዊት የአማራ ልዩ  ሃይል እንዲሁም የህውአት ሰራዊት ጎንደርን በመውረር ቀድመው ህዝቡን የማስፈራራት ስራ  በመስራት ሰልፍ የለም ማንም ወደ ሰልፉ እንዳይመጣ በሚወጡት ላይ እርምጃ  እንወስዳለን እያሉ መግቢያና መውጫውን አጋዚ አጥሮ ቢቆይም ሰአቱ ሲደርስ ግን ጀግናው የጎንደር ህዝብ የተደገነበትን መሳሪያ  ሳይፈራ ግልብጥ ብለው በመውጣት አጋዚን አስለቅቀውት ታላላቅ መልእክቶችን ሲያስተጋቡ ውለዋል።
  3. በጣም ያስደመመም እና ወያኔም አስደንግጦ አይኑን ያስፈጠጠ ልቦናቸውን በጭንቀት የሞላው የማስጣንቀቂያ መልዕክት ጎንደሬዎች አስተላልፈዋል። እንዲም በማለት <<መከላከያ  ሰራዊት እና  የአማራ ልዩ  ሃይል እንዲሁም አጋዚ ህዝቡን የምትደግፉ ከሆነ  ከህዝባችን ጎን ቁሙ አይ የምትሉ ከሆነ  ግን አንድ ጥይት ህዝባችን ላይ ቢተኮስ የገባው ሰራዊት ሳያልቅ በህይወት አይወጣም አጸፋችን እጅግ የከፋ  ነው።>> በማለት ጠንካራ እና ቆራጥ እንዲሁ ብስለት የተሞላበት መልዕክት ማስተላለፋቸው በጣም አስደምሞኛል።

ወያኔዎችም ብርክ ብርክ ያደረጋቸው እና ህዝቡም በአደባባይ የኢትዮጵያን ሰንደቅ አላማ ይዞ  በመውጣት ሳይወዱ በግዳቸው መስማት የማይፈልጉትን ከድንጋጤ ጋር መራራ  እውነት ህዝቡ ሲነግራቸው ዝምታን የመረጡት ለህዝቡ አስበው ሳይሆን ሊደርስባቸው የሚችለውን አጸፋዊ ምላሽ በመፍራት ተገደው እንጂ። የህዝቡም ጥያቄ ጥቂት አንባ  ገነኖች የሚነግሱባት እና  የፈለጋቸውን የሚያደርጉባት አገር ለአንዴ  እና ለመጨረሻ  ግዜ ጠፍቶ ህዝቡ የሚፈልገውን መርጦ   የፈለገው ቦታ ያለአድሎ መኖር የሚችልበትን እና ሁሉም ኢትዮጵያዊ መብቱ የተከበረባት ስርዓት ለማምጣት ለአንባ  ገነኖች   የመጨረሻውን ማስጠንቀቂያ  ቢጫው መብራት በኢትዮጵያ  በሙሉ በርቷል። ቀዩ  እና የመጨረሻው መብራት በቅርብ ቀን የሚበራበት ይጠብቁ። ብራቮ ጎንደር የነጻነት ፋና ያልበገርነት ተምሳሌት ።

ከተማ ዋቅጅራ

01.08.2016

Email- waqjirak@yahoo.com

 

 

Hiber Radio: በጎንደር የአማራ ሕዝብ ያካሄደው ታላቅ የተቃውሞ ሰልፍ በአገር ቤትና በውጭ ታላቅ መነቃቃት ፈጠረ፣ በሳውዲ ያሉ ኢትዮጵያውያን ዕጣ ባይታወቅም ሕንድ ዜጎቿን ልታስወጣ ነው

$
0
0

habtamu05
<...> አክቲቪስት አሚን ጁዲ የኦነግ የፖለቲካ አማካሪ በወቅታዊ ጉዳይ ከሰጡን ቃለ መጠይቅ የተወሰደ (ሙሉውን ያዳምጡ)

ዶ/ር ሙሉጌታ ካሳሁን በቬጋስ የተቋቋመው ቀድሞ የኢትዮጵአ ራዕይ ማህበር ሊቀመንበር ከአቶ አሚን ጁዲ ጋር በጋራ ከሰጡን ቃለ መጠይቅ የተወሰደ (ክፍል አንድን ያዳምጡት)

በአሜሪካ ውስጥ እየተካሄደ ያለው ሰሞነኛው የእጩ ፕሬዝዳንታዊ ተፎካካሪዎች ምርጫ እና ያሰከተለው እንድምታ ሲዳሰስ

አሜሪካዊያን ሙስሊሞች ፣ ጥቁሮች እና ላቲኖች ሰለ ምርጫው ምን የሚሉት ነገር አለ?(ልዩ ጥንቅር)

አቶ መሳፍንት ባዘዘው የቤተ አማራ ም/ሊቀመንበርና የሕዝብ ግንኙነት ሀላፊ (ከህብር ሬዲዮ ጋር ካደረገው ቃለ መጠይቅ ከፍል ሁለት)

17 ኣመት ታክሲ አሽከረከረው አባወራ ዛሬ የሙሉ ጊዜ የሁበርና የሊፍት አሽከርካሪ ስለሆነበት የሰጠው ቃለ መጠይቅ( ቀሪውን ታዳምጡት)

ሌሎችም አሉን

ዜናዎቻችን

በጎንደር የአማራ ሕዝብ ያካሄደው ታላቅ የተቃውሞ ሰልፍ በአገር ቤትና በውጭ ታላቅ መነቃቃት ፈጠረ

ሕዝቡ ወልቃይት የአማራ ነው በኦሮሚያ የሚደረገው ግድያ ይቁም ድንበራችን ተከዜ ነው ድምጻችን ይሰማ ሲል በሕወሃት ላይ ተቃውሞውን አሰምቷል

ሕወሃት የጎንደሩ ታላቅ የእምቢታ የአማራ ሕዝብ ተቃውሞ አስደንግጦታል

የኢትዮጵያዊያኖች እጣ ፈንታ ለጊዜው አለታወቀም፦ሕንድ በሳውዲ አረቢያ ውስጥ በረሃብ የሚማቅቁ 10ሺህ ዘጎቿን ባሰቸኳይ ለታስወጣ ነው

ኢትዮጵያ ዙሪያ ገባዋን በተቃውሞ ማእበል እየተናጠች ነው ተባለ

በእስራኤል የሚገኙ ቤተእስራአላዊያኖች ተቋማዊ በደል እየደረሰባቸው መሆኑን የመንግስት አጣሪ ቡድን አመነ

አለማቀፋዊው የሰደተኖች ተቋም በካይሮ ውስጥ ሰለጠፋው የኢትዮጵያዊቷ ሕይወት ሃዘኑን ገለጸ

የጎንደሩን ተቃውሞ ተቃዋሚዎች ደግፈው መግለጫ ማውጣት ጀመሩ የሚሉና ሌሎችም አሉን

በምስራቅና ምዕራብ ሐረርጌ ሕዝባዊው ተቃውሞ ቀጠለ * በበዴሳ ሰልፈኞች እስር ቤት ሰብረው እስረኞችን አስለቀቁ –በአወዳይ በአጋዚ የተገደሉት ቁጥር 6 ደረሰ

$
0
0

oromo 1 oromo 2

dadar

(ዘ-ሐበሻ) በምስራቅ እና ም ዕራብ ሐረርጌ የህዝብ ተቃውሞ እንደቀጠለ ነው:: ትናንት በአወዳይ ከተማ የአጋዚ ሰራዊት በሕዝብ ላይ ተኮሱ 26 ሰዎች ማቁሰሉና የገደላቸውም ንጹሃን ዜጎች ቁጥር ወደ 6 ማደጉ ተዘግቧል::

በዛሬው ዕለት በአወዳይ አጋዚ አፈሳ የጀመረ ቢሆንም ሕዝባዊው ተቃውሞ በምስራቅ ሐረርጌ ዳዳር ከተማና በማሳላ ከተሞች ተጠናክሮ ቀጥሏል:: ሕዝቡ አንገዛም እስከማለት የደረሰ ሲሆን በሶቃ ከተማና በሌሎችም እየተቃወመ ነው:: በምዕራብ ሐረርጌም እንዲሁ በተለይም በበዴሳ ከተማ የአጋዚ ጦር በንጹሃን ሰላማዊ ሰልፈኞች ላይ ጥይት አዝንቧል:: በዚህም ሳቢያ ህፃናት ሳይቀር እንደቆሰሉና በየአደባባዩም ደም እንደሚታይ ለዘ-ሐበሻ የሚደረሱ መረጃዎች ይጠቁማሉ:: ዘ-ሐበሻ በደም የተለወሱ የቁሰለኞች ፎቶ ግራፎች የደረሳት ቢሆንም እጅግ ዘግናኝ በመሆኑ ፎቶውን ለማሳየት አልቻልንም::

በቆቦ ከተማ በኩል ያለው የሃረር መንገድ መዘጋቱ ሲታወቅ በበዴሳ ከተማ ጥይት የተተኮሰበት ህዝብ ቁጣውን ለመግለጽ እስር ቤት ሰብሮ በመግባት እስረኞችን ማስለቀቁ ተሰምቷል:: በበዴሳ ከተማም በአጋዚ የቆሰሉት ወገኖች ብዛት ከ10 በላይ ሲሆን 2 ሰዎች መሞታቸውም ታውቋል::

በመሰላ ከተማ እና በበበዴሳ ከተማ የቆሰሉ ወጣቶችና ህጻናት በጭሮ ሆስፒታል ህክምና ላይ ይገኛሉ::

መጪው ቅዳሜ  በመላው ኦሮሚያ ሰላማዊ ሰልፍ ይካሄዳል

$
0
0

ከጀዋር መሐመድ

 

በትናንትናው እለት በአማራ ክልል ጎንደር ከተማ በአስርታት ሺዎች የሚቆጠር ህዝብ ሰላማዊ ሰልፍ ወጥቶ ወያኔን ተቃውሞ በሰላም ወደ ቤቱ ተመለሰ። በጣም ጥሩና ታሪካዊ ሰልፍ ነበር። በእለቱ ከጥቂት ሰዓታት በኋል ግን በኦሮሚያ ክልል ምስራቅ ሀረርጌ አወዳይ ከተማ ወጣቶች ሰልፍ ወጥተው በአጋዚ አልሞ ተኳሾች 26ቱ ቆስለው እስከ አሁን 6 ሞተዋል። ይሄንን እንደምሳሌ ጠቀስኩ እንጂ ኦሮሚያ ውስጥ ወያኔ ሰላማዊ ሰልፈኞችን በጥይት እሩምታ ሲፈጅ አዲስ አይደላም። ባለፉት 9 ወራት ካ600 በላይ ዜጎች ተገድለዋል፣ 5000 የሚሆኑ የመቁሰል ጉዳት ደርሶባቸውል። ይሄንን ቁጥር ወስደን ብናሰላው፣ ባለፉት ዘጠኝ ወራት ብቻ በየእለቱ ባማካይ ከሁለት እስከ ሶስት ሰዎች ኦሮሚያ ውስጥ በመንግስት ታጣቂ ሃይሎች ሲገደሉ እንደነበረ ማየት ይቻላል። ይህ ሁሉ ግፍ ሲፈጸም የአምባገኖች ጸባይ ነው ተብሎ ሲታለፍ ነበር። ነገር ግን ሰላማዊ ሰልፍ ሲወጣ የሚገደልው የኦሮሚያ ህዝብ ብቻ መሆኑ ግልጽ እየሆነ ሲመጣ ነገሮችን መለሰን እንድናጤን አድርጎናል። 

File Photo

File Photo

ለመሆኑ በተለያዩ ክልሎች ለወጡ ሰላማዊ ሰልፈኞች የተለያየ ምላሽ ምክንያቱ ምንድ ነው?
1) የኦሮሚያ ሰልፈኞች የጦር መሳሪያ ይዘው አለምውጣታቸው። ምክንያቱም እንደሚታወቀው ባለፉት 25 አመታት ተደጋጋሚ ትጥቅ የማስፈታት ዘመቻ በኦሮሚያ ሲካሄድ ነበር። እናም በግልጽ የታጠቀው ህዝብ አናሳ ነው። በተጨማሪም የኦሮሞ አመራሮች ህዝቡ መሳሪያ ይዞ እንዳይወጣ ሲማጸኑ ነበር። ይሄም የተደረገበት ምክንያት ያቺ ሀገር እና ህዝብ ወደ ዳግም ጦርነት ሳይገቡ በነፍጥ-አልባ ትግል ለውጥ ለማምጣት ካለ ምኞት የተነሳ ነው። ነገር ግን ይህን የኦሮሞን ሰላም ወዳድነት ህወሀቶች እንደ ፈሪነት መቁጠራቸው ገሃድ ወጥቷል።

2) ባለፉት 9 ወራት በኦሮሚያ ውስጥ በተካሄደው ትግል ብዙ ከተሞች ከመንግስት ቁጥጥር ውጪ ሲወጡ እንኳን የትግሬዎች ንብረት እና ህይወት አደጋ ላይ እንዳይወድቅ ከፍተኛ ጥንቃቄ ተደርጓል። ይህ አቋም ግን ሀወሀቶች እንደ ጅልነት (naivity and harmlessness) የተቆጠረ ይመስላል።
ባጠቃልይ የህወሀት መሪዎች እንድን ህዝብ የሚሰሙት በጠመንጃ ሲጋፈጣቸው እና ዘመዶቻቸው ሲነካ ብቻ መሆኑን ደጋግመው አረጋግጠዋል። ለኦሮሞ ህዝባ ያላቸውን መጠን ያለፈ ንቀት እና ጥላቻ በተደጋጋሚ አሳይተዋል። እናም አንድ እጅ ብቻውን ማጨብጨ ስልማይችል የኦሮሞ ህዝብ እራሱን ከተከፈተበት የዘር ማጥፋት ዘመቻ ለመታገድ የስትራቴጂ ለውጥ ሊያደርግ እየተገደደ ነው። ሆኖም ግን ወደዚህ ዓይነቱ መመለሻ የሌለው መንገድ ከመግባታችን በፊት የመጨረሻ እንድል መስጠት አስፈላጊ ሆኖ ተገኝቷል። በዚሁም መሰረት የሚቀጥሉት እርምጃዎች ይወሰዳሉ:

1. በመጪው ቅዳሜ በኦሮሚያ ከተሞች የተቀናጁ ሰልፎች ይካሄዳሉ። እነዚህ ሰልፎች ልክ እንደ ከዚህ በፊቶቹ ሁሉ ፍጹም ሰላማዊ ይሆናሉ። በሰላማዊ ሰልፎቹ ላይ መንግስት ኦሮሞ ላይ እያካሄደ ያለውን ግድያ ባስቸኳይ እንዲያቆም፣ ሁሉም የፖለቲካ እስረኞች ካላንዳች ቅድመ ሁናቴ እንዲፈቱ፣ ኦሮሚያን በኣጋዚ ጦር ማስተዳደር እንዲቆም፣ ህዝቡ ራሱን በራሱ የማስተዳደር መብቱ እንዲጠበቅ የሚሉና የመሳሰሉ ሌሎች መሰረታዊ መብቶችን መከበር የሚጠይቁ ጥያቄዎችና መፈክሮች እንዲንጸባረቁ ይደረጋል።

2. ለዚህ ሰልፍ ፍቃድ አይጠየቅም። በህጉ መሰረት ሰላማዊ ሰልፍ ለማካሄድ የሚያስፈልገው መንግስትን ማሳወቅ ብቻ በቂ ነው። ይህ ጽሁፍ እንደማስታወቂ እንዲረዳ ለኦሮሚያ እና ለፌደራሉ መግስት መሰራቤቶች ገቢ አድርገናል። የኦሮሚያም ሆነ የፌደራል የታጠቁ ሀይሎች ሰላማዊ ሰልፎቹን ለማስተጓጎልም ሆነ በእለቱ በህዝቡ ላይ ጥቃት የሚፈጽሙ ከሆነ ቀጥሎ ለሚመጣው አደጋ ተጠያቂ እንደሚሆኑ በዚሁ ማስጠንቀቅ እንወዳለን። የተቀረው የኢትዮጲያ ህዝብም ለምስክረነት ይህን ግልጽ ማስታወቂያ በጥሞና እንዲያነብልንና ከጎናችንም እንዲሰለፍ ባክብሮት እንጠይቃለን።

የድጋፍ መልክት እና ይትግል ጥሪ –ከጥቁር አንበሳ ዘብ ለኢትዮጵያ የነጻነት ግንባር

$
0
0

tof
እንክዋን ኢትዮጵያን እና ሕዝብዋን ከዚህ ዘረኛ እና ፋሽስታዊ የወያኔ ቡድን ነፃ ለማውጣት ለሚደረገው የነጻነት ትግል ቀርቶ ፡ አንዲት የጽገሬዳ አበባ ለመቅጠፍም እጅ ይደማል።

የኢትዮጵያ ታሪክ በአብዛኛው ለነፃነት የተደረገ የጦርነት ታሪክ ነው። በርካታ ጦርንቶች ተደረገዋል። እነዚህ ሁሉ ጦርነቶች የተካሄዱት ደግሞ የሌላ አገር ድንበር ገፍተን ለመስፋፋት ባለን ዓላማ ሳይሆን የአገራችንን ሉአላዊነት እና አንድነት ያየር የባሕር እና የብስ ይድንበር ወሰናችንን ባጠቃላይ ኢትዮጵያን ከወጪ ወራሪ እና ሰርጎ ገብ ጠላት ለመከላከል የተደረጉ የመከላከል የተደረጉ ጦርነቶች ናቸው። ለዚህ የመከላከል እና የመልሶ ማጥቃት ውጊያ ከግብጾች ፡ ከቱሮክች ፡ ከደርቡሾች ፡ ከእንግሊዞች እና ከጣሊያኖች ጋር በተደጋጋሚ ተዋግተናል። በእነዚህ ሁሉ ውጊያዎች እና ፍልሚያዎች በሚሊዮን የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያንን ሕይወት የቀጠፉብቻ ሳይሆን በዘመናዊ ስንቅ እና ትጥቅ የደራጀውን እና የታጠቀውን ፡ የአውሮፓ ፋሽስታዊ ኃይል በማንበርከክ ሚሊዮን ጀግኖች ኢትዮጵያውያን የተፈጠሩበት እና የጥቁር ሕዝብ የነጻነት አርማ እና ክብር ነው። ይህ ጦርነት ፡ በተለያዩ ጊያዚያቶች እና አቅጣጫአዎች የመጡ ወራሪዎችን አሳፍረው  ፡ የመለሱ ጀግኖች ብቻ ሳይሆን እስከዛሬ በአገሪቱ ውስጥ  ሰላም እና መረጋጋት ጠፍቶ የደከመች እና የተበታተነች ኢትዮጵያን ማየት ለሚፈልጉ አረቦች እና አውሮፓውያን እንዲሁም መሰሎቻቸው የውክልና ጦርነት

የሚያደርጉ ባንዳዎችን እና የባንዳ ልጆችን ወያኔዎችን ፈጥርዋል። እናም ዛሬ እነዚህ የባንዳ ልጆች ናቸው አያት አባቶቻቸው ያልተሳካላቸውን የቅዠት ሕልም ለማሳካት ኢትዮጵያን በብሔር ፡ በሃይምት ፡ በቋንቋ ፡ ከፋፍለው አገርን በመሸጥ ሕዝብን እያተራመሱ ያጥፎት መጥፋት የሽብር ስራ በመስራት የበደኖ ፡ የአርባ ጉጉ፡ የአንኩ እና የጋምቤላው ፡ የአማራው እና የኦሮሞው ፡ ፍጅት የዚህ የባንዳ እና የባንዳው ልጅ ባንዳው ለገሰ(መልስ) ዜናዊ እና አረጋዊ በረሄ እና ግብረአበሮቻቸው ወዘተ የእርኩሰታቸው ራዕይ ውጤት ነው። ዛሬም በኦሮሙያ ክልል ፡ የተጀመረውን ትግል ለማኮላሸት የብዙ ኢትዮጵያውያንን ሕይወት በመቅጠፍ በአማራው ክልል የተነሳውን የማንነት ጥያቄ እና ኢትዮጵያዊ የነጻነት ትግል ለማዳፈን በጎንደር በተለይም በወጣቱ ሃይል የተጀመረው ስርነቀል የነጻነት እንቅስቃሴ ፡ ለማስቆም የተደረገው ትንቅንቅ የእነኚህ ባንዳዎች እና የባንዳ ልጆች የጥፋት እርኩስ መንፈስ ራእይ አስፈጻሚ ውጤት ነው። ወደድንም ጠላንም ፡ ዛሬ በመላው ኢትዮጵያ ብሶት የወለደው የተዳፈነ እሳት በጎንደር ሕዝብ አልበገር ባይነት በጀግንነት እረመጡን ገላልጦ እንደሰደድ እሳት በመቀጣጠል ላይ ይገኛል። ይሂ የግፍ ዋንጫ ሞልቶ ፡ ፈሶ የተጀመረውን ኢትዮጵያዊነት የነጻነት ትግል ምንም ማስቆም የሚችል ምድራዊ ሃይል ከቶ አይኖርም። ይህ ሕዝባዊ አመጽ ፡ ሻጋታው ጸረ ኢትዮጵያ የወያኔ ቡድን ፈጻሜው የመጨረሻው መጀመርያ የመሆኑ አመላካች ነው። በዚህ ታሪካዊ አጋጣሚ የጥቁር አንበሳ ዘብ ለኢትዮጵያ የነጻነት ግንባር ፡ ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ በተለይም ለአማራ እና ለኦሮምያ ክልል ፡ ወያኔን በማስወገድ ለኢትዮጵያ ነጻነት የሚያደርገውን ትግል ያለውን አድናቆት እና ክብር እንዲሁም የትግል አጋርነቱን እየገለጸ ለኢትዮጵያ ሕዝብ ለቀድሞ የመከላከያ ሰራዊ እንዲሁም በውዴታም ሆነ በግዴታ የወያኔን የጥፋት እሜ ለማራዘም ከወንድም እህቶቻቸው ጋር አላስፈላጊ ደም ለተቃቡት የቡድኑ አገልጋይ ወታደሮች የትግል ጥሪያደርጋል።

 

አንደኛ ፡

ውድ የኢትዮጵያ ሕዝብ ወይ ፡ በታሪክህ አይተህው የማታውቀውን ውርደት ፡ ባለፉት የወያኔ የግፍ እና የመከራ አመታት ፡ አይተሃል ፡ ወልደህ ካደክበት ቀዬህ በግፍ ተፈናቅለህ ባይተዋር ሆነህ በሃገርህ እንደሁለተኛ ዜጋ ተቆጥረሃል። በአገርህ በየትኛውም ስፍራ ተዘዋውረህ በነጻነት ሰርቶ የመኖር መብትህን ፡ ተነፍገሃል። በሰላም አብረሃቸው ከምትኖረው ጎረቤቶችህ ጋር በብሔር እና በቋንቋ ሰበብ ተለያይተሃል። ኢትዮጵያዊ በመሆንህ ብቻ ፡ እረሃብ ፡ እስራት ፡ ሞት እና ስደት የአንታ እጣ ፈንታ ሆነዋል። ዝለዚህ ከዚህ የከፋ ውርደት ስለሌለ ሳትውል ሳታድር ለኢትዮጵያ ነጻነት እና ለሰባዊ ክብር ስትል ትግሉን አሁኑኑ ተቀላቀል። ጉልበት ያለህ በጉልበትህ ፡ እውቀት ያልህ በእውቀህ ፡ ገንዘብ ያለህ በገንዘብህ ፡ አረጋዊ እና አዛውንቱ በጸሎት እና ምሕላ ትግሉን አግዙ።

ሁለተኛ፡

ውድ የቀድሞው የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ፡ ለአገር ሉአላዊነት እና አንድነት ፡ ለኢትዮጵያ ሕዝብ ሰላም እና ደህንነት ፡ የክፈለከው የላብ ፡ የደም እና የአካል የሕይወት መስዋእትነት ፡ መና ቀርቶ በወያኔ የኮሎኔል መንግስቱ ኃይለማሪያም እንደግል አሽከር ተቆጥረህ ፡ የደርግ ወታደር እየተባልክ ተዋርደህ እና ተንቀህ ለልመና እና ለእስራት ፡ ለሞት እና ለስደት ፡ የተዳረከው በዚህ ግፈኛ እና ዘረኛ የወያኔ ቡድን ነው። አሁን የወያኔ ግፍ ከልኩ ስላለፈ እብሬቱን ለማስተንፈስ እና ግባ ከመሬቱን ለማፋጠን ፡ ሕዝባዊ ትግሉ ተቀጣጥልዋል። እናም ውርደትን እና ንቀትን የተሸከምክበትን ተከሻ ማሳረፍ ከፈለክ ፡ ሞያዊ ብቃትህን ፡ አይበገሬ ኢትዮጵያዊነትህን የምታሳይበት ወቅት አሁን ስለሆነ በያለህበት አካባቢ ያለምንም ቅድመሁኔታ ፡ ለኢትዮጵያ ነጻነት ሕዝብዊ ትግሉን ተቀላቀል እና ሞያዊ እገዛ አድርግ።

ሶስተኛ፡

የወያኔ ቡድን ያረጀ እና የበሰበሰ ፡ በመሞት ላይ ያለ ቡድን ነው። ምንጊዜም ክፋቶች ያልፋሉ ፡ ሕዝብ ግን ቀጣይ ነው። ስለዚህ የዚህን በመሞት ላይ ያለ ቡድን እድሜ ለማራዘም ፡ ከወያኔ ከሚጣልላችሁ ፍርፋሪ ከርሳችሁን እየሞላችሁ የወገናችሁን ደም በከንቱ የምታፈሱ ፡ በጭቃኔ ሕይወት የምትቀጥፉ እና ወያኔን የምታገለግሉ የሰራዊቱ አባላት ፡ በታሪክ እና በኢትዮጵያ ሕዝብ ተጠያቂ እንደምትሆኑ ከወዲሁ ነገን እያሰባችሁ ፡ ሰልፋችሁን ከሕዝቡ ጋር አስተካክሉ ፡ ለኢትዮጵያ ነጻነት ሕዝባዊ ትግሉን ተቀላቀሉ።

አንደ አገር ፡ አንድ ሕዝብ ፡ አንድ ሰንደቅ ዓላማ እና አንድ የጋራ እድል ኢትዮጵያ።

ሰልፍ የጀግና ድል የእግዚአብሄር ነው።

ከጥቁር አንበሳ ዘብ ለኢትዮጵያ የነጻነት ግንባር።

 

 


ወገኖቻችንን ለዘመናተ የጨረሰው አደገኛው ዘንዶ፡-የኢትዮጵያ ሕገ-መንግስት –ሰርጸ ደስታ

$
0
0

13882704_10206976138181541_4933135800794013649_nየኢትዮጵያውያን ደም ሲገበርለት የኖረው የሕወሐት ኢህአዴግ ታላቅ ጣዖት ሕገ ምንግስት ከዚህ በኋላ ተነኮታኩቶ መሬት ወድቋል፡፡ ብዙዎች ሕገ መንግስቱን ለመናድ በሚል ለጣዖቱ ተገብረዋል፡፡ አምላኪዎቹ ቀን ከሌሊት ይዘምሩለታል፡፡ የኢትዮጵያ ሕዝብ ግን ከምንም በላይ ጠላቱ ይሄ ጣዖት እንደሆነ የገባው ሰሞኑን ነው፡፡ እስከዛሬ እስኪ እናክብረው በሚል ጠጋ ሲሉት ዜጎችን እየጠለፈ ወደሞትና ጉሮኖ የሚያሰገባው ይህ አደገኛ የሕወሐት ኢሕአዴግ አምላክ ዘንዶ (ሕገ-መንግስት) ሰሞኑን ጎንደር ላይ ክፉኛ ቆሰለ፡፡ አምላኪዎቹ መጨረሻ እነሱኑ እንዳይውጣቸው ፈርተው አሁንም ሊላ ግብር ሊያቀርቡለት እጅግ እየተሯሯጡ ነው፡፡ ግን አይመስለኝም፡፡ ዘንዶው መጨረሻ የሚውጠው ሲያጣ ወደ አምላኪዎቹ መዞሩ እውን እየሆነ ይመስላል፡፡ ጎንድር ሁለተኛ እንደይመለስባት አድርጋ አድምታዋለች፡፡ ሌሎችም ብዙዎች አሁን ስልቱን የነቁበት ይመስላል፡፡ በኦሮምያ ብዙ ከዘንዶው ጋር ግብግቡ ቀጥሏል፡፡ ትንሽ የስትራቴጂ ለውጥ ማድረግ የሚያስፈልግ ይመስላል፡፡ ስልቱን ከጎነድሬዎቹ መማር ነው፡፡ ጎንደሬዎቹ ጠመንጃ ስላላቸው ብቻ አይደለም፡፡ በጣም የተቀናጀና ሰፋ ያለ ጉልበት እንዲኖራቸው በጥንቃቄ ነው ድል የተቀዳጁት፡፡ ጎደር ሁሉም አንድ ነው፡፡ ጎደሬዎቹ ኮሌኔል ደመቀን ለጎንደር ፖሊሶች አደራ ሲሰጡ ፖሊሶቹ ኮሌኔሉን ለዘንዶው አሳልፈው እንደማይሰጧቸው ለሕዝቡ ቃል ገብተውዋል፡፡ ሕዝቡም አልተጠራጠረም፡፡ የዘንዶው ሎሌዎች ብዙ ለፍተዋል፡፡ እንዲህ አይነቱ አንድነት በኦሮምያ እስካሁን ልናየው ልናየው አልቻልንም፡፡ አሁን ግን ለኦሮምያ ባለስልጣናትም ይሁን ፖሊሶች ኋላ ተመልሶ ይህ አደገኛ ዘንደዎ እንዳይውጠን ብለው ለራሳቸው ማሰብ ከቻሉ ራሳቸውን ሕዝቡን ይዘው ይከላከሉ፡፡

በአማራ ክልል ኮሚኒኬሽን ባለስልጣን ቀልድ ይሁን የምር አላውቅም ግን ጎንደር ላይ የአምላካችንን ፍላጎት የሚጻረሩ መልክቶች ተላለፈዋል ብለውናል፡፡ የሚያስቀው ይህ ዘንዶ ከሚጠላቸው መልዕክት ተብሎ ባለስልጣኑ ከተናገሩት አንዱ የኢትዮጵያ የነጻነት አርማ አረንጓዴ ቢጫ ቀይ ሰንደቅ አላማችን ነው፡፡ መቼም ጉድ ሳይሰሙ መስከረም አይጠባም አሉ፡፡ አንድ ከምን እንመጣ የማይታወቅ ለዘንዶው እንዲስማማው ተብሎ የኮከብ ቆጣሪዎች ደብተሮች የነገሯቸውን ትልቅ ኮከብ በሰነደቅ አላማችን ላይ ለጠፈው ለዘመናት የሕዝቦችን እኩልነት የሚገልጽ ነው ብለው አጃጃሉን፡፡ እስኪ ይህን ኮከብ አስተውሉት አንድነትን የሚያሳየው የቱ ጋር ነው፡፡ ይልቁንስ ሕዝብን ከሕዝብ በዘር በእምነት እየከፋፈሉ መሆኑን አሳምሮ ይናገራል፡፡ ጠነቋዮቻቸውንም አማክረው ይህን ምልክት ሲያቀርቡለት     ዘንዶው ከራማዬ ወዶት ተቀበሏቸዋል፡፡ እና አቶ ንጉሱ (የአማራው ኮሚኒኬሽን) ራስዎን ቢያድኑ ይሻልዎታል፡፡ ሌላው ዘንዶው እንዳይነኩበት የሚፈልጋቸው ልዩ አምላኪዎቹ (የጣዖቱ ካህናት) በጎንደሬዎቹ የማስጠንቀቂያ መልዕክት ተላልፎላቸዋል፡፡ በእርግጥም የኢትዮጵያ ሕዝብ ሕዋት የሻቢያ ተላላኪ እንደሆነ አሳምሮ ያውቀዋል፡፡ ጎንደሬዎቹ ለዘመናት የተደበቀውን እውነት አደባባይ አወጡት፡፡ የተጠቀሱትም ግለሰቦች በትክክል ሕዝብ ማንነታቸውን አሳምሮ ያውቀዋል፡፡ እውነታው ይሄ ነው፡፡ አቶ ንጉሱ ሕዝብ አይሳሳትም፡፡ የተሳሳቱት እርሶ ነዎት፡፡ ወይም አዚም አርገውብዎት ነው፡፡ ይልቁንም አይፈሩበት ጎንደሬው ነጻነትዎን እያወጀልዎት ነው፡፡

ሌላው ብዙ የትግራይ ተወላጆች አካባቢ ከመቼውም በላይ በአሁኑ ወቅት ለዘንዶው ካሕናት ያላቸውን ወገንተኝነት እያሳዩ ይመስላል፡፡ ከአሁን በኋላ ምንም ሰበብ አይኖራችሁም፡፡ ጎንደሬዎቹ ሁሉንም ናቸው፡፡ ዘር፣ እምነት ምናምን አልያቸውም ሁሉም ጎንደሬዎች ናቸው እንጂ፡፡ ብዙ ጊዜ ብዙ ተመክራችኋል፡፡ አልሰማችሁም፡፡ አሁን ግን ጨው ለራስ ስትል ጣፍጥ አለዚያ የሚላችሁ ጊዜ እንዳይመጣ እፈራለሁ፡፡ ከዘንዶው ራቁ ከኢትዮጵያ ሕዝብ ተቀላቀሉ ብዬ እመክራለሁ፡፡ አሁንም የዘንዶውን ካሕናት የሀሰት ትንቢት እየሰማችሁ ዘንዶው የመሰናበቻው ራት እንዳያደርጋችሁ፡፡ አባይ ጸሐዬ፣ ጀነራል ጻድቃን፣ ኮሌኔል አበበ በፎረሸ ስብከታችሁ ዳግም እናንተ ለምታመልኩት ዘንዶ ኢትዮጵያውያን ጭዳ አይሆኑም፡፡ ምን ይሻላል ብላችሁ ሌሎቹንም የዘንዶው ካሕናት ሰብሰብ አድርጋችሁ ምን አልባት የምትተርፉ ከሆነ ራሳችሁን አድኑ፡፡

ሁሉም የኢትዮጵያ ሕዝብ በአንድነት በዘንዶው ላይ ይነሳ! እስከዛሬ በተገበረለት ወገኖቻችን ይብቃ! የዘንዶው አምላኪዎችም እራሳችሁን ወደ ሕዝብ ማሸሽ የምትችሉበት ጥቂት ሰዓታቶች አሏችሁ፡፡ ከሕዝብ የዘረፋችሁት ሐብት ንብረት እያላችሁ እዛ ስትንደፋደፉ ዘንዶው የመጨረሻ እራቱ እንዳያደርጋችሁ!!!

 

እግዚአብሔር ለኢትዮጵያና ሕዝቦቿ የብርሀን ዘመን ያምጣ!

 

አሜን

 

ሰርጸ ደስታ

 

 

 

 

በአዲስ አበባ የሚገኙ የዘ-ሐበሻ ወዳጆች ይህን ቪዲዮ ቀርጸው ልከዋል –‘አ.አ. መራራ ጩኸት ላይ ናት”

$
0
0

“እንዲህ ዓይነት ድርጊት የሚፈጽም ፋሽት ከሕይወሀት በቀር በዓለም ተነስቶ እንደሚያውቅ መላው ዓለም ይየው” ይላል ቀጥዩን ቭዲዮ ከሃገር ቤት ቀርጸው የላኩት የዘ-ሐበሻ አንባቢዎች:: “ሕገ ወጥ ቤት ሊኖር ይችላል፡፡ ሕገወጥ ከተማ ግን ሰምተን አናውቅም” ሲሉ በቁጭት የሚናገሩት እነዚሁ የዘ-ሐበሻ ወዳጆች አዲስ አበባ ሐና ማርያም; ገብርኤል ሠፈር እና ግራር ሠፈር የፈረሱ ከ20 ሺህ በላይ ቤቶችን እየተዘዋወሩ ቭዲዮ ቀርጸው ሕዝብ ይወቅ ብለው ልከውልናል::

እንደነዚሁ የአንባቢዎቻችን ትንታኔ ከሆነ “ገብርኤል ሠፈር 20 ሺ ቤት የፈረሰበት ሆቴሎች፣ ፖሊስ ጣቢያዎች፣ ትምህርት ቤቶች፣ ግሮሰሪዎች፣ የተገነቡ መንገዶች ፣ አብያተክርስቲያናት፣ ክሊኒኮች የኤሌክትሪክና የውኃ መስመሮች የተሟሉበት ከተማ በፋሽት ሕወሐት እጅ እንዲህ የተፈጥሮ ጥፋት የተፈጸመበት ይመስላል፡፡ ሰሞኑን ቤታቸው በፈረሰበት ሸራ ወጥረው የተቀመጡበት ሚስኪኖች በሽፍቶቹ ወታደሮች ሲደበደቡና ሲባረሩ ሰንብተዋል፡” ይሉና በጨመረሻም ሃሳባቸውን ሲያጠናቅቁ “አዲስ አበባ መራራ ጩኼት ላይ ነች፡፡ የመላውን ኢትዮጵያ እንቅስቃሴ በላም ለማስተናገድ እየተሰናዳች ነው፡፡” ብለዋል:: የት ተሄዶ ይኖራል? ይመልከቱት::

በአዲስ አበባ የሚገኙ የዘ-ሐበሻ ወዳጆች ይህን ቪዲዮ ቀርጸው ልከዋል – ‘አ.አ. መራራ ጩኸት ላይ ናት”

የቀድሞ አየር ኃይል አዛዥ ሜ/ጄ አበበ ተ/ሃይማኖት ሃ/ማርያም ደሳለኝ “የሰራዊት ግንባታ በአብዮታዊ ዴሞክራሲ” የሚለውን መጽሐፍ እንዲያግዱ ጠየቁ

$
0
0

(አበበ ተክለሃይማኖት – ሜጀር ጄነራል)

ግልፅ ደብዳቤ – ለክቡር አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ የጦር ሃይሎች ጠቅላይ አዛዥ

ጉዳዩ – “የሰራዊት ግንባታ በአብዮታዊ ዴሞክራሲ” የሚለው መጽሐፍ ስለማገድ

ክቡር ጠቅላይ ሚኒስቴር

በተለያዩ ግዜያት ለመጠቆም እንደሞከርኩት፤ አንዳንድ ግዜ እንደተቋም ሌላ ግዜ በከፍተኛ መኮንኖች ፀረ ህገ-መንግስት የሆኑ ድርጊቶች እየተስተዋሉ ነው፡፡ የአገራችን መከላከያ ተቋም ሕገ-መንግስቱ እና ሕገ-መንግስቱን ብቻ መሰረት አድርጐ መንቀሳቀስ ሲገባው በግላጭ ሕገ-መንግስቱን የመጣስ ክስተቶች እየታዩ ነው፡፡ አንድ ፀረ-ሕገመንግስት ተግባር ሲጠቆም በማረም ፈንታ በማን አለብኝነት እና በሕብረት በባሰ ሁኔታ እየተደገመ ነው፡፡ለምን? የሰራዊቱ አመራሮች ሕገ-መንግስቱን ጠንቅቀው አያውቁም ብሎ ለማመን አስቸጋሪ ነው፡፡

abebe Tekelehianot

አሁን ስራ ላይ ካሉ ከፍተኛ መኮንኖች፣ በጡረታ ከተሰናበቱ፣ እንዲሁም ‹‹እንከን በሌለው መተካካት›› ከተገለሉ ከፍተኛ መኮንኖች ጋር በተለያዩ ግዜያት የመወየያት እድል ገጥሞኛል፡፡ከወርቃማው የ1997 አጠቃላይ ምርጫ በኋላ ህዝቦችን ለመቆጣጠር የተወሰዱት ፀረ-ዴሞክራሲያዊ ፖለሲዎች፣ መመሪያዎች፣ አሰራሮችና ተግባሮች ወደ መከላከያ ተቋም ገብተዋል እንዴ የሚል ጥያቄ ሲያጭርብኝ ቆይቷል፡፡ ሕገመንግስቱን መፃረር የሰራዊታችንን ሕዝባዊነት ጀግንነት እና ብቃት የሚሸረሽር በመሆኑ እና ሰላማዊ ፖለቲካዊ ትግሉን የሚያበላሽ በመሆኑ ለማንኛውም ኢትዮጲያዊ የሚያሳስብ ነው፡፡

‹‹የሰራዊቱ ግንባታ በአብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ›› የሚለውን መፅሐፍ ሳነብ ግን መሰረታዊ ችግሩ በከፊልም ቢሆን የት ላይ እንደሆነ ሊገለጥልኝ ቻለ፡፡ ሰራዊቱ የገዢው ፓርቲ ርዕዮተ አለም አራማጅ የኢህአዴግ ‹‹የመጨሻው ምሽግ›› እንዲሆን ወይም ‹‹ቀባሪው እንዳይሆን›› መገንባት ከተጀመረ አገሪቱን ወደ  ከፍተኛ ችግር ማስገባቱ የግድ ይሆናል:: የፓርቲው ውስጣዊ ፖለተካዊ እና ዴሞክራሲያዊ ህይወት በተዳከመበት ሁኔታ ደግሞ ሰራዊቱ የተወሰኑ አመራሮች “የመጨረሻ ምሸግ” ይሆናል ማለት ነው፡፡

በመከላከያ ሚኒስቴር ስር በሚገኘው “ብራና ማተሚያ ድርጅት“ የታተመው መፅሐፍ 209 ገፆች ያሉት ሲሆን ሕገ-መንግስቱን እና “አብዮታዊ ዴሞክራሲ“ የሚለውን ርዕዮተ ዓለም በማደባለቅና በማምታት ስለሰራዊት ግንባታ ይዘባርቃል::

ክቡር የጦር ሃይሎች ጠቅላይ አዛዥ

የመፅሐፉ ርዕስ ‹‹የሰራዊት ግንባታ በአብዮታዊ ዴሞክራሲ›› ነው የሚለው፡፡ ሰነዱ ከርዕሱ ጀምሮ ምን ማለት መሆኑ ቢታወቅም የበለጠ ግልፅ ለማድረግ የተለያዩ ጥቅሶችን ማስቀመጥ ይበጃል በሚል ጥቂት ጥቅሶችን እንዳቀርብ እንዲፈቀድልኝ በትህትና እጠይቃለሁ፡፡

የመከላከያ ኃይል ግንባታ አላማችን በሚል ንዑስ-ርዕስ ሥር፡-

‹‹እኛ የያዝነው አላማ እና ተግባራዊ እያደረግነው ያለ መደብ በሃገራችን አብዮታዊዴሞክራሲያዊ ለውጦች እንዲካሄድ ይህ ስርአት ስር እንዲሰድ ማድረግ ነው፡፡›› (ገፅ 20)

 ‹‹እኛ የምንገነባው የመከላከያ ኃይል የአብዮታዊ ዲሞክሪሲያዊ ስርአታችን ዘብ ነውብለን በግልፅ እና በጥሬው ማስቀመጥ አስፈላጊ ነው›› ይላል ምን አይነት እብሪት ነው(ገፅ 22)

‹‹ለአንድ ፓርቲ ዘብ በመሆን መልክ ሊገልፅ ይችላል፡፡ ከፓርቲው ውጭ ሆነም ስርአቱንእንደስርአት ሕግመንግስት  እና ሕገመንግስታዊ ስርአቱን በመጠበቅ አንፃር ሊገለፅይችላል፡፡›› (ገፅ 23)

‹‹በእኛ ተጨባጭ ሁኔታ የአብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ ስርአታችን ደህንነት መከላከልማለትና የሃገር ደህንነት መከላከያ ማለት በመሰረቱ አንድ ነው ማለት ይቻላል፡፡አብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ ስርዓት ከሌለ ፈጣንና ቀጣይነት ያለው ኢኮኖሚያዊ፣ማህብራዊ ልማት፣ ዴሞክራሲያዊ አንድነት .. አይኖርም፡፡ ይህ ከሌለ ደግሞ ሀገሪቱመጨረሻ ወደ ሌለው ቀውስና ግጭት ገብታ መበታተን ነው፡፡ ስለሆነም ሀገሪቱ  እንደሀገር መቀጠል የምትችለው በአብዬታዊ ዴሞክራሲ ነው ማለት ይቻለል፡፡ ከዚህአኳያ ሲታይ ሀገራችንን መከላከልና አብዬታዊ ዴሞክራሲያዊ ስርአትን መከላከልአንድና የማይነጣጠሉ ነገሮች ናቸው ማለት ይቻላል፡፡›› (ገፅ 25-26)

‹‹ስለሆነም ለእኛ የሃገራችንንና የአብዮታዊ ዴሞክራስያዊ ስርአታችንን ደህንነትመከላከል (መጠበቅየተለያዩ ነገሮች አይደሉም፡፡አብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ ስርአታችንከሌለ የኛ የምንላት ሃገር አትኖርም›› (ገፅ 27) 

‹‹የምንገነባቸው በመከላከያ ኃይል አላማው የስርአታችንን ደህንነት መጠበቅ ነው ሲባልየሚገነባውና የሚመራው የስርአቱ መሪ የሆነው አካል ብቻ መሆን አለበት ነው›› (ገፅ28)

‹‹የመከላከያ ኃይላችን ግንባታ ስራ አላማው ምን እንደሆነና ከዚህ የሚመነጩየመከላከያ ኃይላችን ባህሪያት ምን እንደሚሆኑ በግልፅ ለያይቶ ማስቀመጥ በዚያችቁርጥ ቀን ማለት የስርዓታችን ህልውና በመከላከያ ኃይላችን ብቃትና ምንነት ላይበምትንጠላጠልበት ጊዜና ወቅት አስተማማኝ መከላከያ ምሽግ መሆኑን በማረጋገጥበኩል ወሳኝ ሚና ያለው ጉዳይ ነው፡፡›› (ገጽ 31)

‹‹ጉዳዩ በአብዮታዊ ዲሞክራሲ ስርዓቱ በመጨረሻ መከላከያ ምሽግ የሌለው ስርዓትሆኖ እንዳይቀር በማድረግ ወይም በመከላከል ጉዳይ ብቻ ሳይሆን ጠባቂዬና አለኝታዬብሎ የሚለው ሰራዊት ተመልሶ ቀባሪው ሆኖ እንዳይገኝ የማድረግ ጭምር ነው፡፡›› (ገጽ81)

ክቡር ጠቅላይ ሚኒስቴር

የኢትዮጵያ መከላከያ ተቋም የአብዮታዊ ዴሞክራሲ ብሎም የኢህዴግ ‹‹ጠባቂ›› እንዲሆን – በሌላ አነጋገር የጥቂት ሰዎች ‹‹ጠባቂ›› እንዲሆን – በተለያየ መንገድ በጭንቀት፣ በልመና የተደጋገመው ጸሎት አይሉት ምህላ በጣም እንደሚሰለች ይገባኛል፡፡ ይቅርታ ይደረግልኝ፡፡ እኔም ስልችት እያለኝ ደጋግሜ ያነበብኩት የመከላከያ ተቋሙ በምን መልኩ ከህገ-መንግስታችን ተጻራሪ ሆኖ እየሰራ  መሆኑን እንዲያሳይ ነው እንጂ፡፡

መጽሐፉ ሕገ-መንግስታችንን በውል መጥቀስ የጀመረው በገጽ 87 ነው፡፡ የአብዮታዊ ዲሞክራሲ “የቁርጥ ቀን” መከላከያ መሆኑን በተደጋጋሚ ካስረገጠ በኋላ በ2.1 ሕገመንግስታችን እንደ ሰራዊታችን ግንባታ መነሻ በማለት ማብራራት ይጀምራል፡፡ መዘባረቁን በማያሻማ ሁኔታ እየቀጠለ ፀረ ዲሞክራቲክ አስተሳሰብ ደግሞ ከደርግነት ባላነሰ መንገድ ሲገልጸው እንደገና “ኢህአዴግ ከሌለ ይህች ሀገር የለችም” በሚለው  አባባል ሲያመላልሰው ይታያል፡፡

እባክዎ  እንደገና ከመጽሐፉ በስፋት እንድጠቅስ ይፍቀዱልኝ፡-

ህገ– መንግስታችን  ለሰራዊት የፖለቲካ ግንባታ ስራችን ወሳኝ መነሻ ነው የምንለውህገመንግስታችን ሰራዊቱ የህገመንግስቱ ታማኝ ጠባቂ መሆን አለበት በማለት በግልጽስለሚያስቀምጥ ብቻ አይደለም፡፡ ሌሎች ዲሞክራሲያዊ ስርዓቶች እንዲህ ዓይነትአካሄድ ስለተከተሉም አይደለም፡፡ ይልቁንም ይህ አባባል በሕገመንግስታችን በግልፅእንዲቀመጥ የተደረገበት ዋነኛ ምክንያት ህገመንግስቱ የአብዮታዊ ዲሞክራሲያዊስርዓት ጠባቂ የሆነ ሰራዊት ለመገንባት ለሚካሄደው የፖለቲካ ግንባታ ስራ በቂና ብቁመነሻ እንዲሆን ስለታመነበት ነው ማለት ይቻላል፡፡

ቀደም ብሎ እንደተመለከትነው በሁሉም አገሮች በመከላከያ አቅም በሚገነባው አንድንስርዓት ከውስጥና ከውጭ ጠላቶች ለመከላከል ተብሎ ነው፡፡ በእኛ ሁኔታም የተለየዓላማ ሊኖረው አይችልም፡፡ እኛ የምንገነባው ሰራዊት አብዮታዊ ዲሞክራሲያዊስርዓታችንን ከውስጥና ከውጭ ጠላቶች ለመከላከል ተብሎ በሚገነባ ሰራዊት ብቻ ነውመሆን የሚችለው፡፡ በአሁኑ ወቅት አብዮታዊ ዲሞክራሲያዊ ስርዓታችን እና ኢህዴግተለያይተው ሊታዩ የሚችሉ አይደሉም፡፡ የሊበራል ዲሞክራሲ አስተሳሰብ የበላይነትበነገሰበት ወቅት ሁሉም ፓርቲዎች ማለት ይቻላል መሰረታዊ የሊበራል ዲሞክራሲአስተሳሰቦችን ተቀብለው በዚህ ዙሪያ ብቻ ነው የሚለያዩት በየጊዜው እየተቀየሩ ወደስልጣን ቢመጡም በስርዓቱ ላይ የሚመጣ መሰረታዊ ለውጥ የለም፡፡ ስለሆነም ስርዓቱከእያንዳንዱ ፓርቲ ተለይቶ የሚታይና ሊታይ የሚገባው ይሆናል፡፡ (ገጽ 88 – 89)

ክቡር የጦር ሃይሎች ጠቅላይ አዛዥ

የ1997 ምርጫ ህዝቦቻችን ዕድል ሲያገኙ ምን ማድረግ እንደሚችሉ ያሳየ ነው፡፡ በቀጣዩ ምርጫ ለምሳሌ መድረክ ቢያሸንፍ የመከላከያ ሰራዊታችን የኢህአዴግ የቁርጥ ቀን በመሆን መድረክን ስልጣን እንዳይቆጣጠር ይከላከላሉ? ጠበንጃቸውን በህዝቦች የተመረጠ እና በህዝቦች ላይ ያዞራሉ ማለት ነው? መድረክ በሊበራል አስተሳሰቦች ዙረያ የተደራጀ በመሆኑ በምርጫ ከአሸነፈ አሁን ያለውን መከላከያ ተቋም እንዳለ አፍርሶ ሌላ የራሱ ሊገነባ ማለት ነው? የሆነ ፓርቲ በሰላማዊ  መንገድ ባሸነፈ ቁጥር በሚፈርስና በሚገነባ የመከላከያ ተቋም ታይቶም ተሰምቶም አያውቅም ፡፡ ለተወሰኑ ሰዎች ለኢህዴግ ሃላፊዎች ሲባል አገራችንን ለማፍረስ መዘጋጀት ማለት እኮ ነው፡፡

ይህ አስተሳሰብ አብዮታዊም ዲሞክራሲያዊም አይደለም፡፡ በእኔ አረዳድ አብዮታዊ ዲሞክራሲ “ሊበራል ዲሞክራሲ መራመድ እስከሚችለው ጫፍ መውሰድ ነው”፡፡ በሌላ አነጋገር አብዮታዊ ዲሞክራሲ ከሊበራል ዲሞክራሲ በላይ ዴሞክራሲያዊ ነው፡፡ የህዝቦቻችን የመወሰን ስልጣን በተሻለ የሚያምን ነው፡፡ እኛ ካልተመረጥን አገሪቱ ገደል ትግባ የሚል የጽንፈኞች አስተሳሰብ መሆን አልነበረበትም፡፡

ክቡር የጦር ሃይሎች ጠቅላይ አዛዥ

በዚህ መፅሐፍ ውስጥ በእውነትና በቅንነት የታመነበት ቢሆን አብዮታዊ ዲሞክራሲ ምን ማለት እንደሆነ ትርጓሜ ይሰጠው ነበር፡፡ በአሁኑ ጊዜ የአብዮታዊ ዲሞክራሲ ምንነት በአንዳንድ ከፍተኛ ባለስልጣናት ደረጃ ሳይቀር የማይታወቅ መሆኑን በየቀኑ በቴሌቪዥንም በአካል እየተስተዋለ ነው፡፡

አንድ ቀን ያጋጠመኝን ላካፍልዎ፡- ሶስት ሆነን ስለ ኢትዮጵያ ሁኔታና ስለአንድ መሪ ስናወራ የልማት መሪም አርበኛም (Champion) ናቸው በሚል ተስማማን፡፡ አንዱ ተነስቶ የልማት አርበኛ ብቻ ሳይሆኑ የዴሞክራሲያዊ ሻምፒዮን ናቸው አለ፡፡ ሶስተኛው ተነስቶ ‹‹እስኪ አብራራው›› አለው፡፡ በጥርናፈ (Centralism) ያምናል አለን:: አፈርን! ተሳቀቅን! ግን ስለዴሞክራሲ ያለው አመለካከት እስከዚያ ድረስ የወረደ መሆኑን በየቀኑ የምናየው ክስተት በመሆኑ አዝነን፤ ይህች አገር ወዴት እየሄደች ነው አልን፡፡

ክቡር ጠቅላይ ሚኒስቴር

አሁንም በተለያዩ መንገድ የአገር መከላከያ ተቋም እና የኢህዴግ አባላት የስራቸውና የአኗኗራቸው ሁኔታ የተለያየ በመሆኑ መጠነኛ የአቀራረብ ልዩነት ይኖር ይሆን እንጂ አንድ ናቸው በማለት በገጽ 100 – 101 እንዲህ ይላል፡፡

‹‹በሰራዊታችን የምናካሂደው የፖለቲካ ስራ የአብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ ፖለቲካዊግንባታ ሰራ ነው፡፡ ስለሆነም በመሰረታዊ የአፈጻጸም አግባብ በድርጅታችን ውስጥከምናካሂደው የግንባታ ሰራ የተለየ አይሆንም፡፡ ይህ እንዳለ ሆኖ የሰራዊቱ እና የኢህዴግአባላት የስራቸውና የአኗኗራቸው ሁኔታ የተለያየ መሆኑ አይቀርም፡፡ ከዚህ የተነሳበሁለቱም የግንባታው ሰራ አፈጻጸም አንዳንድ ልዩነቶች ሊኖሩት የግድ ነው፡፡ በዚህፅሁፍ የአብዮታዊ ዲሞክራሲ ፖለቲካ ግንባታ ሰፊ መሰረታዊ አፈጻጸሞችን እንዳለ ነውየምንወስደው፡፡ የሚዲያው ሰራ በገዛ ራሱ ለህብረተሰቡ በሚዘረጋውና ሰራዊቱምእንደማንኛውም ሰው በሚሰማው ወይም ገዝቶ በሚያነበው በመንግስትና በድርጅትሚዲያ አማካይነት ሊፈጸም ይችላል፡፡” (ገጽ 116) 

ክቡር ጠቅላይ ሚኒስቴር

በመጽሐፉ ውስጥ የተለያዩ ጥያቄዎችን ለማንሳት የሚያስችሉ የተዘበራረቁ ጉዳዮች አሉ፡፡

“እኛ” ብለው ስለሰራዊታችን ግንባታ የሚጽፉት አመራሮች “የቁርጥ ቀን” ደራሽ እንዲሆንላቸው በአብዮታዊ ዴሞክራሲ ሽፋን በማላወስ እኛን አገልግሉ ከማለት ውጭ ያስቀመጡት የተለየ የግንባታ ዓላማዎች እና አቅጣጫዎች የሉም፡፡ ከሞላ ጎደል “በኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ እና የብሔራዊ ደህንነት ፖሊሲ” ሰነድ ላይም የተቀመጡ ናቸው፡፡ በአደባባይ ለህዝብ በዚያ ሰነድ ላይ ግን “የአብዮታዊ ዴሞክራሲ ወይም ኢህዴግ የመጨረሻ መከላከያ ምሽግ አይልም” ለምን?

ሕገ-መንግስቱ በሰላም እስኪታገሉ ድረስ ህገ-መንግስቱ ራሱን በማሻሻል መብት የሚያስቀምጥ ነው፡፡ ከበላይ ህጋችን አኳያ ሁሉም በሰላም የሚንቀሳቀሱ ፓርቲዎች እና የህብረተሰብ ክፍሎች እኩል ናቸው፡፡ በሰራዊቱ ልዩ ጥበቃ የሚያስፈልገው ፓርቲ ወይም የሚገለል ወይም የሚመታ ፓርቲ የለም፡፡ የሚገርመው ነገር ግን በአሁን ጊዜ አብዛኛዎቹ የተቃዋሚ ፓርቲዎች እና የህብረተሰብ ክፍሎች ‹‹ህገ-መንግስቱ ይከበር›› ሲሉ የህገ-መንግስቱ አቀንቃኝ የነበረው ኢህዴግ በግላጭ ሲሸረሸር እና “አብዮታዊ ዴሞክራሲ”ን እንደ አድሃሪያን መሸሸግያ ሲጠቀምበት በጣም ያሳዝናል፡፡ ገዥ ፓርቲ በመሆኑ ደግሞ ያስፈራል፡፡

አብዮታዊ ዴሞክራሲ የሚል “ምትሓተኛ” አስተሳሰብ እንዳለና እጅግ እንደላቀ ልዩ ነገር “Mystify” ተደርጎ የማይተነተን፣ የማይታወቅ፣ ሰው በጭፍን እንዲያምነው የሚደረግ ሙከራ አሳሳቢ ነው፡፡ እኔ እስከሚገባኝ ድረስ አብዮታዊ ዲሞክራሲ ይሁን ሊበራል ዲሞክራሲ ሁሉም ካፒታሊሰታዊ ስርዓት ለመገንባት ዓላማ አድርገው ነው የሚንቀሳቀሱት ያውም እስከ “ነጭ ካፒታሊዝም” ተብሎም ነበር፡፡ በካፒታሊስት ስርዓት ከማንም በላይ ተጠቃሚዎች ካፒታሊስቶች ናቸው፡፡

እስከሚገባኝ አብዮታዊ ዴሞክራሲ በሚገባ ከተተገበረ የገበሬዎች፣ የላብአደሮች ፣ሌሎች ዝቅተኛ የሕብረተሰብ ክፍሎች ጥቅም በሚረጋገጥበት መንገድ ስርዓቱን ሊመራ ይችላል፡፡ ሃብት በመፍጠር ሂደት ክፍፍሉ በተቻለ ደረጃ ፍትሃዊ ማድረግ ነው፡፡ እንደዛውም ሆኖ አሁንም ዋናው ተጠቃሚ ካፒታሊስቱ ነው፡፡ አሁን እየተመዘገበ ያለው ኢኮኖሚያዊ ዕድገት ብቻ እንኳን ብናይ ሁሉም የህብረተሰብ ክፍሎች ተጠቃሚዎች ቢሆኑም በሀብታም እና ድሃ ያለው ልዩነት በጣም እየሰፋ ከመሄድ አላገደውም፡፡ ባልሆነ ተስፋ በማይመስል አስተሳሰብ አገር እንዳይጎዳ መጠንቀቅ ጥሩ ነው፡፡

በገጽ 126 ያለውን እስኪ እንየው፡-

ሁሉም በተራ ውትድርና እንዲያልፍ የሚደረግ አሰራር ከሰራዊታችን ባህሪ ጋር የሚሄድብቻ ሳይሆን ለሰራዊታችን የተለያዩ ጥቅሞችም የሚያስገኝ ይሆናል፡፡ ከሁሉ አስቀድሞይህ አሰራር ከአብዮታዊ ዲሞክራሲ በከፍተኛ ደረጃ የማይጠቀሙ ወገኖች ወደ ሰራዊቱለመግባት ፍላጎት እንዳይኖራቸው የሚያደርግና በአንጻሩ በስርዓቱ በከፍተኛ ደረጃተጠቃሚ የሆኑ ወገኖች ብቻ ሰራዊቱን እንዲቀላቀሉ የሚያደርግ አካሄድ ነው፡፡››

ይህ ደግሞ ሌላ hypocrisy ይመስለኛል፡፡ ከስርዓቱ በከፍተኛ ደረጃ የማይጠቀሙ ወገኖች ሲባሉ እነማናቸው? መሳፍንት? አሁን የሉም የመሳፍንት ልጆች፡፡ እረ ተዉ! ኢሰፓ የነበሩ? እነሱም ወሳኝ ሚና የላቸውም፡፡ የሚቀሩት ገበሬ፣ ላብአደር፣ ምሁርና ካፒታሊስት ወዘተ ናቸው፡፡  ገበሬው መቼም አይታሰብም፤ ላብአደር ተጠቃሚ ተብሏል፤ ካፒታሊስቱ የለም – እሱማ ዋናው ተጠቃሚ ነው፤ ምሁሩ? አረ እንጃ እንዳይፈነግላቸው እየፈሩ ካልሆነ እሱም በጣም ተጠቃሚ ነው፡፡

ታዲያ በከፍተኛ ደረጃ የማይጠቀሙ ወገኖች እነማ ናቸው? ፖለቲካዊ ስርአቱ የራሱን ችግር ላለማየት (externalize) ለማድረግ የሚደረድራቸው ጠላቶች እንዳይሆኑ? ትምክህትና ጠባብነት በህብረተሰቡ በሚታዩ ኋላቀር አስተሳሰቦች ናቸው፡፡ የተወሰኑ ልሂቃን ይህን በህብረተሰቡ ያለውን ኋላቀር አስተሳሰብ መሰረት አድርገው ለራሳቸው ጥቅሞች ሲሉ ሰላማዊ ፖለቲካዊ ስርአቱን እንዲናጋ ያደርጋሉ፡፡ እነዚህንም ቢሆን በጣም ጥቂቶቹ ናቸው፡፡ ለነሱ መሰረት የሚሆነው የዴሞክራሲ አሰተዳደር እጥረት ነው፡፡ እነዚህን ለማግለል ሲል ደግሞ የሰራዊቱን ሙሁራዊ አቅም እየገደለ እንዳይሆን መፈተሹ ተገቢ ነው፡፡

ወደ ሰራዊታችን በመጀመሪያ የሚሰለፈው ከ 18 – 23 አመት አካባቢ ያለ ወጣት ነው፡፡ የወላጆቹን የመደብ ጀርባ እያዩ ላለማስገባት ሲባል ከ10ኛ ክፍል በመመልመል በሚደረግ የሰራዊት ግንባታ ሂደት ከፍተኛ አመራር ለመፍጠር የሚደረግ አካሄድ አደገኛ እንዳይሆን መጠንቀቅ ያስፈልጋል፡፡ የተማረ ሰው የመጥላት አዝማሚያ እንዳይሆን፡፡

“እኛ” በቀዳማዊ ኃይለስላሴ አነጋገር አንድ ሰው ነው:: ምናልባትም ንጉሳዊ ቤተስብ ይሆናል፡፡ “እኛ” ማለት ከአንድ ሰው በላይ ቢሆን ማነው? 36ቱ የኢህአዴግ ስራ አስፈፃሚ? የኢህዴግ ምክር ቤት አባላት? 7 ሚሊዮን የሚሆኑት አባላት ቢሆኑስ? የአብዮታዊ ዴሞክራሲ አስተሳሰብ ልእልና እንዳልነገሰ መፅሃፉ በተደጋጋሚ ይገልፅልናል፡፡ ይህ ማለት ቢያንስ ከ85 ሚሊዮን በላይ ህዝባችን፤ ሰራዊታችን የአብዮታዊ ዴሞክራሲ የመጨረሻ ምሽግ እንዲሆን አልወሰነም፡፡ ‹‹የሰራዊት ግንባታ በአብዮታዊ ዴሞክራሲ›› ላይ ያለው እኛ” አድሃሪ ነው፣ፀረ-ዴሞክራቲክ ነው፣ ፀረ-ህገመንግስት ነው፡፡

ክቡር ጠቅላይ ሚኒስተር  እና የጦርሃይሎች ጠቅላይ አዛዥ

በእኔ አመለካከት ሰራዊታችን የህዝቦቻችን እና የአገራችን አለኝታ የሚሆነው ህገመንግስቱንና ህገመንግስቱን መሰረት ተደርጎ የሚወጣ ፖሊሲ፣ መመሪያ፣ አሰራር እና ግንባታ ሲኖር ነው፡፡ ‹‹የአብዮታዊ ዴሞክራሲ የመጨረሻ ምሽግ ነው›› ሲባል ግን የሰራዊቱ ምልመላ፣ የስልጠና፣ የዝውውር፣ የእድገት፣ የጡረታ ማራዝም፣ በመተካካት የሚገለሉበት ሂደት እንዲሁም አጠቃላይ የሰራዊት ግንባታው “በአብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ” መዝሙር በሚዘምሩ፣ “የአብዮታዊ ዴሞከራሲ” ወሬ በሚያቀብሉ እና ህገመንግስቱን በግላጭ የሚጥስ አባላት ያለበት ሰራዊት እንዳይሆን ስጋት አለኝ፡፡ በአጠቃላይ ከህዝቦቻችን በተለይም ደግሞ ከፖለቲካ ድርጅቶች የሚኖረውን ግንኙነት በጣም አሳሳቢ ያደረገዋል፡፡

የኦሮሞ ህዝቦች ለመብታቻው ባደረገት ዴሞክራሲያዊ እንቅስቃሴ ለደረሰው ጉዳት እርሶዎ ይቅርታ ሲጠየቁ በኢትዮጵያ ውስጥ ባልተለመደ መንገድ ህዝብን የሚያከብር በመሆኑ ለህዝብ ይቅርታ ማለት ፈር ቀዳጅ በመሆንዎ ብዙዎቻችን ኮርተናል፡፡ የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብት ኮሚሽን የተወሰደው እርምጃ “ተመጣጣኝ” ነው ሲል እንደገና አፈርን፣ ፓርላማው ሲያፀድቀው የባሰ ተሸማቀቅን፡፡ ዴሞክራሲ አስተዳደርን በማበላሸት ዋናው ተጠያቂ የኢህአዲግ መንግስት ሆኖ እያለ በዜጎች ላይ የደረሰው ጉዳት ተመጣጣኝ ሲባል ያሳዝናል፡፡ እነዛ የሞቱት የቆሰሉት የታሰሩት በሙሉ አሸባሪዎች ናቸው ማለት ነው?

በአጠቃላይ የስርአቱ ጉዳይ ግን  እጅግ አሳሳቢ ነው፡፡ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤታችን ስለመከላከያ በየግዜው የሚገመግመው “እንደ መከላከያ የለም” የሚያሰኝ ነው፡፡ እንደ ‹‹የሰራዊት ግንባታ በአብዮታዊ ዴሞክራሲ›› ያለ መሰረታዊ የግንባታ ዶክመንት እና ህገመንግስቱን በሚፃረር መንገድ የሰራዊቶቻችን ግንባታ ሲካሄድ “ዓይኑ እንዳላየ” “ጆሮው እንዳልሰማ” ማወደስ የማይሰለቸው ተቋም በመሆኑና በእርስዎ የሚመራው የብሄራዊ ደህንነት ምክር ቤትም ከዚህ አኳያ ቢፈተሽ መልካም ይመስለኛል፡፡

ይህ የሰራዊት ግንባታ መጽሐፍ፡- ሰራዊታችን የአብዮታዊ ዴሞክራሲ የመጨረሻ ምሽግ ነውየሚለው አስተሳሰብ፤ ኢህአዴግ ከሌለ የኢትዮጵያ ህዝቦች የሉም፤ የዚህች አገር ችግሮችበኢህአዴግ ብቻ እና ብቻ ይፈታል፤ አብዮታዊ ዴሞክራሲ ከሌለ አገር የምንለው የለም፣ የሚሉ ሀሳቦች፤ በተለይም የህገ መንግስት ምሰሶ ከሆኑት አንዱ ተቋም የሆነው መከላከያችን ከየትኛውም ዓይነት የፖለቲካ ድርጅት ወገንተኝነት ነፃ ይሆናል የሚለውን እና የሕገ -መንግስቱ አንኳር የሆነውን የመድብለ ስርአት ግንባታ የሚጻረር በመሆኑ ይወገድ፡፡ ነገር ግን መጽሐፉ የህገ መንግስት ጠማማ አተረጓጎም ለአገር ጥፋት እንዴት እንደሚውል የሚያሳይ በመሆኑ እኛም ልጆቻችንን እንድንማርበት በሙዝየም ውስጥ ይቀመጥ፡፡ በአስቸኳይ የማስተካከያ እርምጃ እንዲወሰድ፣ አጠቃላይ የመከላከያ እንደ ተቋሙ እንዲፈተሽ እና Re-indoctrination እንዲደረግ እንደማንኛው ዜጋ በትህትና እጠይቃለሁ፡፡

“ያበራሽን ጠባሳ ያዬ በእሳት አይጫወትም፡፡”- ነፃነት ዘለቀ

$
0
0

ነፃነት ዘለቀ (nzeleke35@gmail.com)

የሀገራceን ዕጣ ፋንታ በሕወሓት እጅ ሥር ከገባ  በትንሹ ሩብ ምዕተ ዓመት ደፍነን ወደ ግማሽ ምዕተ ዓመት እየገሠገስንነው፡፡ የዕዝ ጉዳይ ሆኖ የቀን ጎደሎ ገጠመንና እኛም ሀገራችንም በመጥፎ ስኬቶች እየተንበሸበሽን ዛሬ ላይ ደረስን፡፡ መስያሚያ ጆሮና መመልከቻ ዐይን በሌላቸው ወንድሞቻችን እየተረገጥንና በከፋፍለህ ግዛው እንግሊዛዊ የአገዛዝ ሥልት እየታመስን ብዙ ባጀን፡፡ ሆኖም ግና ሁሉ ነገር እንደሚጀመር ማለቁም አይቀርምና ይህ ከፋፋይ የወያኔ ሥርዓት-አልባ ሥርዓት ወደማይቀርለት ታሪካዊ ግብኣተ-መሬት ሊወርድ እያኮበኮበ መገኘቱ ለወዳጆቹ ቀርቶ ውድቀቱን ለሚመኙና ለውድቀቱም ለሚሠሩ የነፃነት ፋኖዎች ግልጽ የሆነ ይመስላል፡፡13882704_10206976138181541_4933135800794013649_n

ነገር ግን ሟች ይዞ ይሞታል ይባላልና ከዚህ እንደነቀርሣ ውስጣችንን በልቶ ከጨረሰን ፋሽስታዊ ሥርዓት በቀላሉ መገላገል የምንችለው ተበዳዮች ነን የምንል ወገኖች በተለይ ልዩ ዘዴ ቀይሰን ስንታገልና ንጹሓን ወገኖቻችን እንዳይጠቁ ስንከላከል ነው፡፡ በገበያ ግርግር ሌባ ይበራከታል፤ ሌባ ደግሞ የማመዛዘን ችሎታና የኅሊና ጤናማነት የለውም፡፡ ስለሆነም በግርግር ወቅት ለጉዳት የሚዳርግን ማናቸውንም ዓይነት የሥጋት ምንጭ አስቀድሞ ማድረቅ ተገቢ ነው፡፡ አለበለዚያ ጸጸቱ ለማይበርድ ከፍተኛ አደጋ መጋለጥ ይኖራል፡፡

ከሥጋት ምንጮች አንዱ ከዚህ ቀጥዬ የምነግራችሁ ነው፡፡ በደንብ ተረዱልኝ!

በሩዋንዳ ጭፍጭፋ ጊዜ ሕዝቡ አለውድ  ጎሣውን የሚገልጽ የመታወቂያ ወረቀት በግዴታ ይሰጠው ነበር፡፡ የዚያ ዓይነት ከሩዋንዳ ይልቅ ለጠባብ ዘር ቅድሚያ የሰጠ አሠራር ያስከተለውን መዘዝ በወቅቱ ታዝበናል፡፡ ሁቱዎች ቱትሲዎችን እንደዐይጥ እየጨፈጨፉ ሲጨርሷቸው በአብዛኛውና ለመለየት የሚቸገሩትን ሰው መታወቂያ እንዲያሳይ በማስገደድ መታወቂያው ላይ “ቱትሲ” የሚል የዘውግ ስም ካዩ በያዙት ገጀራ  ባልተለመደ ጭካኔ ቀረጣጥፈው ይገድሉት ነበር፡፡ በ21ኛው መቶ ክፍለ ዘመን እንዲህ ያለ መታወቂያ ላይ ከዜግነት ባለፈ ዘርን የሚጠቁም መንግሥታዊ ሥርዓት ሲያጋጥም መረገም እንጂ የሥልጣኔ ምልክት አይደለም፡፡ ከዚህ አንጻር እኛም ተረግመናል፡፡

የሀገራችን ጉግማንጉጎች በዚሁ የለዬለት አፓርታዳዊ አሠራር በየመታወቂያችን ላይ “ዐማራ፣ ትግሬ፣ ኦሮሞ፣ ጉራጌ፣ ሀረሪ….” እያሉ ጽፈውበታል፤ “የተለዬ ዘር የለኝም፤ ‹ኢትዮጵያዊ› ብለህ/ሽ ጻፈው/ፊው” የሚልን ሰው በነፍጠኛነትና(የፈረደበት ዐማራነት) በቀድሞዋ ኢትዮጵያ ናፋቂነት እየፈረጁ ለስቃይና እንግልት ዳርገውታል – እንዲህ የሚልን ሰው ትግሬም ይሁን ኦሮሞ መታወቂያው ላይ “ዐማራ” ተብሎ እንዲጻፍበት ያደርጋሉ፡፡ በዚህ ጦስም ብዙዎች በተለይም በአገር አቋራጭ አውቶቡስ ተሣፍረው ሲሄዱ መንገድ ላይ በሚያጋጥሙ የተደራጁ ሽፍቶች አማካይነት አለርህራሄ ተጨፍጭፈዋል – መታወቂያን በዘርና በሃይማኖት መፈረጅ ጉዳቱ ከባድ ነው(የሃይማኖቱን ሰማዕትነት ነው ብንለውም እንኳን)፡፡ በግድያና በጭፍጨፋ ለሚያምን አይሲሳዊ ኃይል ዜጎችን በዚህ መልክ በጎሣ ፈርጆ በመታወቂያ ሞታቸውን ማወጁ ለጭራቆቹ ትልቅ እገዛ ማድረግ ነው፡፡ ዜጎችን በመታወቂያቸው ላይ በዘር መቦደን ለወፈፌ ጠላት ጭዳ ማድረግና የጥፋት ሥራቸውን በግማሽ እንደማቃለል ነው፤ ቋንቋቸውን የሚችል ሰው እንደምንም አሳምኖ ማምለጥ ሲችል በመታወቂያው ብቻ ይጠቃል ማለት ነው፡፡

ስለዚህ በኢትዮጵያ ያላችሁ የቀበሌ መስተዳድሮችና የወያኔው ባለሥልጣናት በምታምኑት ይሁንባችሁ ይህን መታወቂያ ነገ ዛሬ ሳትሉ አሁኑኑ ለውጡት፡፡መታወቂያ ላይ ከተፈለገ የደም ዓይነት እንጂ የዘር ማንነት አይጻፍም፤ ነውርና ወንጀልም ነው፡፡ አንደኛ አንድ ሰው የጠራ ማንነት ላይኖረው ይችላል – በአባቱ ኦሮሞ በእናቱ ትግሬ በአያቱ ዐማራ ቢሆን ይህ ዓይነቱ ሰው አንድ የዘር ሐረግ መዝዞ እንዲጠራበት ወይም እንዲታወቅበት ማድረግ አይቻልም፤ እርሱም አይፈልግ ይሆናል – ያለመፈለግ መብቱንም መጣስ ሰብኣዊ መብትን መጨፍለቅ ነው፡፡ ሁለተኛ ዘውጋዊ ማንነት በባለቤቱ ዘንድ መቅረት ይገባዋል እንጂ ከሀገራዊ ዜግነት በዘለለ መታወቂያ ወረቀት ላይ አስቀምጦ በኩራት ሊኮፈሱበት የሚገባ ጀብድ አይደለም፤ ማንም በፍቃዱ መርጦ ዐማራ ወይ ትግሬ – ይህን ወይም ያን አይሆንምና፡፡ ስንት ጅልነት አለ!

ስለዚህ ይህን ዓይነቱን ከድንቁርና ወይም ከተለዬ ድብቅ ፍላጎት የመነጨ አሠራር በአስቸኳይ መለወጥና ዜግነት በሚል ቦታ ላይ “ኢትዮጵያዊ” ብቻ ብሎ መጻፍ ከፊት ለፊት የተጋረጠን አደጋ በእጅጉ መቀነስ እንደሚቻል መረዳት ተገቢ ነው፡፡ ነገረ ካለፈ በኋላ መቆጨት አይጠቅምም፡፡ ከአሁኑ መጠንቀቅ ተገቢ ነው፡፡ ሁሉም ዜጋ ይህን ወቅታዊ ማሳሰቢያየን በየሄደበት በማስተጋባት መንግሥት ተብዬው በዐይን የማይታይ ረቂቅ ተቋማችን መታወቂያ እንዲለውጥልን ጫና ይደረግበት፡፡ ደግሞም ይቻላል፡፡ አንዳንዴ ዜጎችን ማዳመጥ ተገቢ ነው፡፡ በጥላቻ ታውሮ ምንም አስተያየት ላለመቀበል ጆሮን መጠቅጠቅ ጉዳቱ ከፍተኛ ነውና ወያኔዎች እባካችሁን በዚህ ነገር አስቡበትና አፋጣኝ እርምጃ ውሰዱ፡፡ በውጭ ሀገራት ያላችሁ ወገኖቻችንም ይህ ጉዳይ በቀጥታ ባይመለከታችም ወገኖቻችሁና ዘመድ አዝማዶቻችሁ የዚህ ሸውራራ ወያዊ ሤራ ሰለባ ይሆናሉና ለዓለም አሰሙልን፤ በሩዋንዳ ለተከሰተው ዕልቂት አንደኛው መራጃ ይሄው በመታወቂያ ላይ ዘውግን የመጻፍ አላስፈላጊ ጣጣ ነበር፡፡ እርግጥ ነው – ወያዎች ይህን ያደረጉት የሥራ ዕድሎችን ከማከፋፈል አኳያ የማይፈልጉትን ዘውግ ከማዕዱ ለማራቅና እንዳስፈላነቱም ከዚያ ለከፋ አደጋ በቀላሉ ለመዳረግ እንደሆነ ግልጽ ነው፡፡ ሆኖም ይህ ነገር በእንግሊዝኛው የቃል አጠቃቀም backfire  ሊያደርግና ካሰቡት ውጪ የጎንዮሸ ጉዳት እንደሚኖረው አልተረዱትም፡፡ ወያኔዎች በጥቅምና በሥልጣን ጥማት ያበዱ፣ በቂም በቀልና በጥላቻ የሰከሩ ደምባራዎች ስለሆኑ የፊት የፊቱን እንጂ የአህያን ያህል አንድ አሥር ሜትር ያህል እንኳን ወደፊት ራቅ አድርገው መመልከት የማይችሉ፣ ዕውቀትና ጥበብ በራቸውን የጠረቀሙባቸው የአስተሳሰብ ድሆች ናቸው፡፡ ለማንኛውም “ያበራሽን ጠባሳ ያዬ በእሳት አይጫወትም፡፡”ና ልብ ያለው ልብ ይበል፡፡ የእሳትን አስከፊ ጉዳት ለማየት በግድ እጅን ወደነበልባላዊ እቶን መክተት አይጠበቅብንም – ቀድሞ ከተቃጠለ ሰው መማር አስተዋይነት ነው – ሊያውም በነፃና እንደክፍያም ከታሰበ ከከንፈር መጠጣ ባልዘለለ የሀዘን ስሜት ብቻ፡፡

ኢትዮጵያዊነት የብሄር/ብሄረሰብ ጥያቄና ፌዴራሊዝም ! –ፈቃዱ በቀለ (ዶ/ር

$
0
0

የኢትዮጵያውያን ፎረም በአውሮፓ ባዘጋጀው በዴን ሀግ ከተማ  ከ28.07-30.07.2016 በሚደረገው     የኢትዮጵያውያን  የስፖርትና የባህል መድረክ ላይ ለውይይት የቀረበ ጥናት ! መልካም ንባብ!!     

  ፈቃዱ በቀለ (ዶ/ር)

መግቢያ !
13882497_10206705956951835_2221566154745392193_nአብዮቱ ከፈነዳ ከ1966 ዓ.ም ጀምሮ ህዝባችን ሰላምና እረፍት ማግኘት አልቻለም። አብዮቱ ሲፈነዳ፣ የንጉሳዊ አገዛዝ ሲፈርስ፣ የሱ መሰረት የሆነው የፊዩዳሉ ስርዓት ሲደመሰስ ሰፊው ህዝብ የነፃነት ብርሃንን የማየት ዕድል አጋጥሞት ነበር። እስከተወሰነ ደረጃም ድረስ ነፃነትን በመጎናጸፍ እንደቆመበት የህብረተሰብ ክፍል የየራሱን ማህበራዊ ተቋም መመስረት ችሎ ነበር። ይሁንና ግን ይህ የተጎናጸፈው ድልና የተስፋ ብርሃንን ማየት ከውስጥ ከዚህና ከዚያ ብቅ ባሉ ድርጅቶች፣ ግን ደግሞ ዕውነተኛ ዓላማቸው በማይታወቅ ኃይሎች በመወጠርና ጦርነት ውስጥ እንዲገባ በመገደዱ አገሪቱ እስካሁን ድረስ ጋብ ሊል ያልቻለ ትርምስ ውስጥ እንድትወድቅ ተገደደች።

በመሰረቱ አብዮቱ ሲፈነዳ የሁሉንም የህብረተሰብ ክፍሎችና፣ እንዲሁም ደግሞ በብሄረሰብ ነፃነት ስም የሚታገሉ  ድርጅቶችን ጥያቄዎች መመለስና ማስተናገድ የሚችል ነበር። እንደሚታወቀው በአገራችን ምድር የዲሞክራሲ መብትና የመሬት ለአራሹ ጥያቄዎች ሲነሱና እስከተወሰነ ደረጃም ድረስ መልስ ሊሰጣቸው ሙከራ ሲደረግ፣ የጥያቄዎቹ አነሳሰም ሆነ ተግባራዊ የማድረጉ ጉዳይ ከዘጠና በመቶ በላይ የሚሆነውን ህዝባችንና ልዩ ልዩ ድርጅቶችንም የሚያካትትና በጋራ እጅ ለእጅ ተያይዞ ለመተርጎምና ቀስ በቀስ ነፃነትን ለመቀዳጀት የሚያስችል ሂደት ነበር። ይሁንና ግን የአብዮቱ መፈንዳት፣ የንጉሳዊው አገዛዝና የሱ መሰረት የሆነው የፊዩዳል ስርዓት መገርሰስና ልዩ ልዩ የጥገና ለውጦች ቀስ በቀስ ተግባራዊ መሆን ከረጅም ጊዜ አንፃር ሲታይ ዕድገትንና ነፃነትን ሊያመጣ የሚችለውን አካሄድ ያልተገነዝቡ ኃይሎች በመሰረቱ በወታደራዊ አገዛዙ ላይ ሳይሆን በህዝባችን ላይ በመዝመት አገራችንን ትርምስ ውስጥ ለመክተት ችለዋል። ከሰላሳ ዓመታት በላይ በየቦታው የተካሄደው ጦርነት አገሪቱን ውጥረት ውስጥ መክተቱ ብቻ ሳይሆን ከፍተኛ የሰውና የሀብት ውድመት እንዲፈስ አድርጓል። ካለማወቅና በሰፊው ካለማሰብ የተነሳ ከዚህ ብሄረሰብ ነው የመጣሁት፣ ስጨቆን ነበር ፣ ስለዚህም የምፈለገው ሌላ ነገር ሳይሆን „ነፃነቴን“ ብቻ ነው በማለት የተካሄደው እልክ አሰጨራሽና የወንድማማቾች ርስ በርስ መተላለቅ አገራችን ዛሬ ላለችበት አስከፊና እጅግ አስቸጋሪ ሁኔታ ከፍተኛውን አስተዋፅዖ አድርጓል ማለት ይቻላል።

በአገራችን ምድር ከሃያ አምስት ዓመታት ጀምሮ ስልጣን ላይ ቁጥጥ ያለውና፣ የአገራችንና የህዝባችንን የመኖርና ያለመኖር ዕድል የሚወሰነው የወያኔ አገዛዝ በቡሃ ላይ ጆሮ ደግፍ ተጨምሮበት እንደሚባለው አነጋገር አገራችንን በብሄረሰብ በመከለልና የክልል ፖለቲካ ተግባራዊ በማድረግ ህዝባችን በአንድነት ተነሳስቶ በጋራ አገሩን እንዳይገነባ አድርጎታል። የሚሆነውን የማይሆነውና፣ ከታሪክ ጋር ግኑኘት የሌላቸውን ነገሮች በማውራትና የጥላቻ መርዙን በመርጨት ምስኪኑ ህዝብ ርስ በርሱ እንዳይተማመን አድርጓል። በተለይም ወያኔ ስልጣን ከያዘ ጀምሮና ይህን ዐይነቱን የከፋፍለህ ግዛና የጥላቻ ፖሊሲ ሲያዳምጥ ያደገ ወጣት የኢትዮጵያዊነት ስሜት ላይሰማው ይችል ይሆናል። ስለሆነም ከዚህኛው ወይም ከዚያኛው ብሄረሰብ ነው የመጣሁት በማለት ርስ በርሱ እንዳይግባባና በጎሪጥ እንዲተያይ ለማድረግ ተችሏል። በመሆኑም አብዛኛው ወጣት የመለያ ቀውስ(Identity Crisi)እንዳለበት ግልጽ እየሆነ መጥቷል።  በእርግጥም ወያኔ ስልጣን ከጨበጠ ጀምሮ ለተወለደ ልጅና በወያኔ የትርምስ ፖለቲካ ውስጥ ላለፈና ጭንቅላቱ ውስጥ ካካተተ ወጣት የኢትዮጵያዊነት ጉዳይ ሊምታታበት ይችላል። በተለይም ደግሞ በምድር ላይ የሚታየው የኢኮኖሚና የማህበረዊ ጉዳይና የተወሰነውም የህብረተሰብ ክፍል በገንዘብ መናርና መባለግ አዲስ ታዳጊ ወጣት ስለህብረተሰብና ስለኢትዮጵያዊነት ምንነት ሊምታታበት ይችላል። በዚህም የተነሳ በብዙዎቻን ዘንድ የሚነሳው ጥያቄ የአገራችንና የህዝባችን የወደፊት እጣ ምን ይሆናል? ኢትዮጵያስ ባለችበት መልኳ ልትቀጥል ትችላለች ወይ? ወይስ ሌሎች የአፍሪካ አገሮች ውስጥ እንደሚታየው በአገራችንም ምድር የእርስ በርስ መተላለቅ በመከሰት አገራችን አሁን ባለችበት መልኳ ልትቀጥል ትችላለች ወይ? የሚለው ነገር እያሳሰበን መጥቷል። የነገሩን አሳሳቢነት ለመረዳት አንዳንድ የተሳሳቱና ከታሪክና ከህብረተሰብ ግንባታ ጋር ሊያያዙ የማይችሉ ነገሮችን በማንሳት ዛሬ አገራችን ለምን ይህ ዐይነቱ ሁኔታ ላይ ለመድረስ እንደቻለች ለመወያየት እንሞክር።

 

የህብረ-ብሄር ምስረታ አስፈላጊነትና የብሔረሰብ ጥያቄ ጉዳይ በአጠቃላይ !

እንደሚታወቀው በህብረተሰብ ታሪክ ውስጥ ብሄረሰቦች የሌሉበት አገርና የተለያዩ ብሄረሰቦች ሳይጋቡና ሳይዋሃዱ እያንዳንዱ ብሄረሰብ በራሱ ክልል ብቻ ተወስኖ የኖረበት ማህበረሰብ በፍጹም የለም። የሰው ልጅ ውስጣዊ ኃይል(Dynamism) ስላለው በአንድ ቦታ ረግቶ ሊኖር በፍጹም አይችልም። በተለይም በአንድ አካባቢ የስራ-ክፍፍልና ገበያ የሚባሉት ነገሮች ሲዳብሩ፣ የዚህ ወይም የዚያ ጎሳ ተወላጆች ከሌላ አካባቢ በመምጣት የተቀረው እዚያ በመጋባትና በመዋለድ፣ እንዲሁም አዲስ የስራ ባህል ሲለምድና ገቢ ሲያገኝ ድሮ ከነበረበት የጎሳ ወይም የብሄረሰብ ስንሰለት በመላቀቅ የአስተሳሰብ አድማሱ ይሰፋል። እንደዚህ ዐይነቱ የህዝብና ወይም የግለሰቦች እንቅስቃሴ የማይታየው ወይም በጥቂት ብቻ የሚካሄደው በከብት አርቢነት ሙያ በሚተዳደሩና፣ ዘላን እየተባሉ በሚጠሩ ጎሳዎች ዘንድ ነው። የእንደነዚህ ዐይነት ጎሳዎች እጣ ደግሞ እግዚአብሄር የሰጣቸውን የመፍጠር ኃይል ለመጠቀም አለመቻል ብቻ ሳይሆን፣  በተለያየ ጊዜ ከተፈጥሮ በኩል የሚመጣባቸውን አደጋ መቋቋም አይችሉም። ህይወታቸውም ተደጋጋሚና አሰልቺ ሰለሚሆን የመፍጠር ኃይላቸው ውስን በመሆን አዳዲስ መሳሪያዎችን በመስራት ኑሮአቸውን መልክ ሊሰጡትና ወደ ተሻለ የአኗናር ስልትና ዕድገት ደረጃ ላይ ሊሸጋገሩ በፍጹም አይችሉም።

በተለያዩ የታሪክ አጋጣሚዎች ሆኖ በአንድ ክልል ውስጥ ከሚኖሩት ውስጥ፣ እስከዚህም ድረስ በአንድ ቋንቋም ሆነ በባህል ካልተሳሰሩት ውስጥ አንደኛው የህብረተሰብ ክፍል ወይም ጎሳ በባህል፣ ቋንቋን በማዳበርና የአገዛዝ መዋቅርን በመዘርጋትና፣ በመጀመሪያ ደረጃ በአካባቢው ያለውን የጥሬ-ሀብትንና መሬትንም ጭምር በመቆጣጠር ከራሱ የተውጣጡ ብሄረሰቦችንም ወደ መበዝበዝ ያመራል። ግብር(tribute) እንዲከፍሉ ያስገድዳል። የተወሰነውንም ለጦር በመመልመል ከውጭ የሚመጣበትን ወራሪ ኃይል መክቶ በመመለስ የበላይነትን ይቀዳጃል። በአካባቢው ሌላ አገዛዘ እንደዚህ ካለ በጉልበት ለማስገበር ይሞክራል፤ ወይም በመጋባትና ርስ በርስ በመተሳሰር አገዛዙን ያስፋፋል። በህብረተሰብ ውስጥ በሚደረግ ማህበራዊ እንቅስቃሴ(Social Mobility) በተለይም በንጉስ መልክ በተዋቀረ አገዛዝ ከአንድ ጎሳ ብቻ በመውጣጣት የበላይነቱን ይዞ ሊቆይ አይችልም። ከአንድ ጎሳ የተውጣጣ አገዛዝ ወይንም ኤሊት በጎሳው ላይ የበላይነቱን ይዞ ሊቆይ የሚችለው በክላን በሚተዳደርና ገና ባልተሰበጣጠረና(Undifferenciated or non-segmented) በስራ-ክፍፍል ባልዳበረ ማህበረሰብ ውስጥ ብቻ ነው። ስለሆነም በንጉስ መልክና በፊዩዳላዊ ስርዓት ስር በተዋቀረ አገዛዝ ውስጥ ባለው ቅራኔና ሬሶርስን ለመቆጣጠር በመፈለግ የተነሳ በተለያየ አካባቢ የሚገኙ ከተለያዩ ንዑስ-ጎሳዎች የተውጣጡ የገዢ መደቦች ርስ በርስ በመጋባት የጎሳ ውስንነት ቀስ በቀስ ይደመሰሳል።

ይህ ዐይነቱ ከተለያየ አካባቢ የተውጣጡ የገዢ መደቦች ርስ በርስ መጋባትና የአገዛዝ መዋቅርን ማስፋፋት በአውሮፓ ምድር የተሰፋፋና የተለመደ ነበር። በተለይም በእንግሊዞችና በፈረንሳዮች የገዢ መደቦች መሀከል መተሳሰርና መጋባት ነበር። በሌላ ወገን ደግሞ በዕድገትና በአስተዳደር ቀድመው የሄዱ ግን ደግሞ ገና ወደ ህብረ-ብሄር(Nation-State) ደረጃ ላይ ያልደረሱ አገሮች፣ ሌሎች በዕድገት እስከዚህም ያልገፉ አገሮችን በመውረር ህልውናቸውን ለመደንገግ በቅተዋል። ጀርመን እ.አ በ1871 ዓ.ም በአንድ ግዛት ውስጥ ከመጠቃለሏ በፊት በስዊደን፣ በዴንማርክ፣ በአውስትሪያና በፈረንሳይ ተደጋጋሚ ጦርነት ተከፍቶባትና እስከተወሰነ ጊዜያትም ድረስ በተለይም የተወሰነው የጀርመን ክፍል በፈረንሳይ አገዛዝ ቁጥጥር ስር ነበር። እንደዚሁም እንግሊዝ  የካቶሊክ ሃይማኖት ተከታይ የሆነውን የሰሜኑን አየርላንድ ህዝብ በማስገደድ የተወሰነው አልቀበልም ሲል ደግሞ ከመሬቱ በማፈናቀልና ተከታይ የሆናቸውን የስኮቲሽንና እንግሊዛዊያንን በማስፈር የኋላ ኋላ አየርላንድ የካቶሊክንና የፕርቴስታንት ሃይማኖት ዕምነትን በሚከተሉ በመከፋፈል አንድ ጎሳ በሃይማኖት የተነሳ ሊለያይ በቅቷል። በጊዜው የእንግሊዝ ዋና ዓላማ የስራ ኃይል ለመፈለግና የአየርላንድንም ሪሶርስን ለመቆጣጠር ስለነበር የተከተለው ዘዴ  አንድን ህዝብ በሃማኖት መከፋፈልና እንዲጠላሉ ማድረግ ነበር።  የኋላ ኋላ ልዩነቱ እየከፋ በመሄድ አንድ ወንድማማች ህዝብ ርስበርሱ ለረጅም ዓመታት እንዲጨራረስ ተደረገ።  የአውስትሪያው የሀብስበርግ ሞናርክያዊ አገዛዝም የተለያዩ ጎሳዎችን በጉልበት በማጠቃለል ነበር በአንድ በኩል አገዛዙን ለማሰፈን የቻለው። በሌላው ወገን ደግሞ ከረጅም ጊዜ አንፃር ሲታዩ ለህብረ-ብሄር ምስረታ ሊሆን የሚችል መስረት በወረረባቸው አገሮች ውስጥ በመጣል እንደ ሀንጋሪ የመሳሰሉ አገሮች ራሳቸውን እንዲችሉ ለማድረግ የበቃው። የሀብስበርግ ሞናርኪያዊ አገዛዝ ከተደመሰሰ በኋላ አውስትሪያ ወደ ሪፑብሊክነት በመሸጋገርና አገዛዟን ውስን በማድረግ ዲሞክራሲያዊ ስርዓት የሰፈነባት አገር ለመሆን በቃች። ዛሬ የምናየውንም የዕድገት ደረጃ ላይም ለመድረስ በቃች። በዚህ ዐይነቱ ተሻልን የሚሉ አገዛዞች ባደረጉት ጦርነትና መስፋፋት የግዴታ በህዝቦች ዘንድ መቀላቀልንና መዋለድን አስከትሏል።

በአውሮፓ የህብረተሰብ ታሪክ ውስጥ የህብረ-ብሄርን ወይም በአንድ አገዛዝ መጠቃለልንና የሪፑብሊክን መመስረት ልዩ የሚያደርገው፣ የታሪክ አጋጣሚ ሆኖ በተለያዩ ኤፖኮች ጭንቅላትን የሚያድስ ምሁራዊ እንቅስቃሴዎች መካሄዳቸው ነው። በተለይም በጣሊያን ምድር ሬናሳንስ የሚባለው ምሁራዊ እንቅስቃሴ ከመከሰቱ በፊት የኢጣሊያን ህዝብ አንድ የሚግባባበት  ቋንቋ ስላልነበረውና፣ ለዕድገት አስቸጋሪም ስለነበር ዳንቴ የሚባለው ፈላስፋ ህዝቡ የሚግባባበትን አንድ ቋንቋ በመፍጠርና ተግባራዊ በማድረግ ለሬናሳንስ እንቅስቃሴ ተቀዳሚ ስራ በማዳበር እምርታ ሊሰጠው ችሏል። ሬናስንስ የሚባለው እንቅስቃሴ ሲጀምር፣ ሲስፋፋና ሲዳብር የዕደ-ጥበብ ስራ፣ ንግድና የከተማ ግንባታዎች በመስፋፋት ህዝባዊ እንቅስቃሴ በመዳበር  ተሰበጣጥሮና በተለያየ ጎሳ ተከፋፍሎ ይኖር የነበረው የኢጣሊያን ህዝብ በመሰባሰብ የስልጣኔ ባለቤት ሊሆን ችሏል። ይሁንና ግን ከካቶሊክ እምነት ለመላቀቅ ያልቻለው የኢጣሊያን ህዝብ በካቶሊክ የገዢ መደቦችና በቀሳውስት በመሰቃየት እንደ እንግሊዝና፣ ሆላንድ፣ የኋላ ኋላ ደግሞ እንደ ፈረንሳይና ጀርመን ሙሉ በሙሉ ሪፑብሊክን በመመስረት አንድ ህዝብ ሊሆን አልቻለም። ከውስጥ በነበረው የገዢ መደቦች ሽኩቻ የተነሳ ጣሊያን በወጭ ኃይሎች ልትወረርና በሪናሳንስ አማካይነት የተቀዳጀችውን ስልጣኔ በጠቅላላው በጣሊያን ምድር ሙሉ በሙሉ ተግባራዊ ማድረግ አልቻለችም። ይህ ዐይነቱ ልዩነት እስከዛሬም ድረስ በተለይም በሰሜኑና በደቡቡ ኢጣሊያን  ክፍል መሀከል ጎልቶ የሚታይ ሀቅ ነው።

ወደ ሌሎች አገሮች ስንመጣ የህብረ-ብሄር ምስረታ የተለያየ መልክ የያዘ መሆኑ እንረዳለን። የእንግሊዚን የህብረ-ብሄረሰብ አመሰረራት ለየት የሚያደርገው፣  የህብረ-ብሄረሰብ ምስረታው ሳይንስና ቴክኖሎጂን የዕድገት መሰረት ለማድረግ በሚፈልጉት የፕሮቴስታንት መሪዎችና፣ ሳይንስንና ቴክኖሎጂ፣ እንዲሁም አጠቃላይ ዕድገት እንዳይኖር በሚቃወሙት በካቶሊክ እምነት ተከታዮች መሀከል የተካሄደ የጦፈ ትግል ሲሆን፣ በተጨማሪም በመሬት ከበርቴው፣ በአሪስቶክራሲውና በሌላ ወገን ደግሞ እያደገ በመጣው የኢንዱስትሪና የንግድ ከበርቴ መሀከል ነበር። የካቶሊክ ሃይማኖት ተከታዮችና ቄሶች፣ የመሬት ከበርቴዎችና አሪስቶክራሲው የነበራቸውን ስታተስ ላለማጣት ሲሉ ለውጥ እንዳይመጣ አግደው ይዘው ነበር። ይህ ሁኔታ ደግሞ እንግሊዝን አንድ ወጥና ጠንካራ መንግስት ሆና እንዳትወጣ አግዶ ሲይዛት፣ እንግሊዝ ሀብቷን ወደ ሮም ላለው የካቶሊክ አገዛዝና ስፔይን የምታስተላልፍ ነበርች። ይህ ሁኔታ በዚህ መቀጠል እንደሌለበት የተረዱት የቱዶር ሞናርኪዎች ሃይንሪሽ ሰባተኛውና ስምንተኛው፣ በተለይም በሬናሳንስ ዕውቀት የሰለጠነው ሃይንሪሽ ስምንተኛው የእንግሊዝ ንጉስ በሮሙ የካቶሊክ ሃይማኖት ህግ የሚገዛ ሳይሆን በራሱ እንደሚገዛና ነፃም እንደሆነ በማወጅ የመጀመሪያውን የካቶሊክን ሃይማኖት የበላይነት ዕምነት ይሰብራል።  ይሁንና ግን አብዮቱ እስከፈነዳበት እስከ 1642-1651 ዓመት ድረስ የፊዩዳሉና የአሪስቶክራሲው መደብ የበላይነት ያያለበትና ለዕድገትም እንቅፋት በመሆኑ የጥገና ለውጥ በሚፈልጉት ፓርሊያሜንታሪያንና በንጉሳዊ አገዛዝ ተከታዮች ዘንድ የጦፈ ጦርነት በመካሄድ ለመጨረሻ ጊዜ የካቶሊክ ሃይማኖት የበላይነት በመሰበር የከበርቴውን መደበ የበላይነት ይረጋገጣል። ለማኑፋክቱር አብዮት እንዲያም ሲል ለካፒታሊዝም ዕድገት የሚያመች ሁኔታ ይፈጠራል። ይህ የጥገና ለውጥና ከዚያ በኋላ የማኑፋክቱር አብዮት መካሄድና የገበሬው መደብ ከመሬት እየተፈናቀለ መምጣትና ወዝአደር መሆን የእንግሊዝ ህዝብ እንዲሰበጣጠርና በአንድ አገዛዝ መዋቅር ስር እንዲጠቃለል አድርጎታል።  በሌላ አነጋገር ለአንድ ህብረ-ብሄር ምስረታና ለካፒታሊም ዕድገት እንቅፋት የነበረው የካቶሊክ ሃይማኖትና የመሬት ከበርቴውና አሪስቶክራሲው፣ እንዲሁም የበላይ ጠባቂያቸው የሆነው ንጉሳዊ አገዛዝ ከተደመሰሰ በኋላ ነው እንግሊዝ ቀስ በቀስ ወደ ኢንዱስትሪ አብዮትና ወደ ካፒታሊዝም ዕድገት ለመሸጋገር የቻለቸው። በዚህም አማካይነት ነው ወደ ህብረተሰብ ምስረታ ልታመራ የቻለችው።

ወደ ጀርመን ስንመጣ ጀርመንም እስክ 1871 ዓ.ም ደረስ ከሶስመቶ በላይ በሚቆጠሩ መሳፍንት የምትተዳደርና በውጭ ወራሪ ኃይሎች የምትሰቃይ ነበረች። ይህ በዚህ መቀጠል እንደሌለበት የተረዳው የፕረሺያ የንጉሳዊያን አገዛዝ አልገዛ ያሉትን በኃይል በመውረር፣ ሌሎችን ደግሞ በጥቅም በመግዛት የመጨረሻ መጨረሻ ወደ አንድ ግዛትነት ልታመራ ችላለች። ማርቲን ሉተር መጽሀፍ ቅዱስን እስካተመበትና የፕሮቴስታንትን ሃይማኖት እስካወጀና የህዝቡ የማሰብ ኃይል በትምህርት አማከይነት መዳበር አለበት ብሎ መስበክ እስከጀመረበት ድረስ ጀርመንም በጎሳና በሃይማኖት የተከፋፈለች ነበረች። መጽሀፍ ቅዱስ ወደ ጀርመንኛ ቋንቋ ሲተረጎምና አድባራት የሃይማኖት መማሪያ ተቋሟት መሆናቸው ቀርቶ ወደ ህዝብ መማሪያነት ሲለወጡ የህዝቡ ኃይል መሰብሰብና የማሰብ ኃይሉም መዳበር ይጀምራል። የመፍጠር ችሎታውም ያድጋል። በዚህ አማካይነት የፕሮቴስታንት ሃይማኖት በተስፋፋባቸው አካባቢዎች  የንግድ እንቅስቃሴና የዕደ-ጥበብ  ሙያዎች ይዳብራሉ፤ ይስፋፋሉም። በተለያዩ ጊዜያት የወጡ ጥናቶች እንደሚያረጋግጡት ከሆነ ቀደም ብሎ የፕሮቴስታንት ሃይማኖት የተስፋፋባቸው አካባቢዎች የካቶሊክ ሃይማኖት ተከታይ ከሆኑት አካባቢዎች ጋር ሲወዳደሩ በዕውቀትም ሆነ በቴክኖሎጂ፣ እንዲሁም በንግድ እንቅስቃሴና ከተማዎችን በመገንባት በብዙ እጅ ቀድመው እንደሄዱ ነው። ይሁንና ግን አገሮች በአንድ ግዛት ውስጥ ሲጠቃለሉ ሁሉም አካባቢዎች ወይንም ክፍላተ-ግዛቶች የግዴታ አንድ ወጥ ትምህርትንና ተመሳሳይ የሆኑ ለቴክኖሎጂ ዕድገት የሚያመቹ ሙያዎች ዕውቀቶችን በመቀበል ዕድገታቸው ተመጣጣኝ እየሆነ ሊመጣ ችሏል።

በአጠቃላይ ሲታይ በአውሮፓ ምድር ውስጥ የህብረ-ብሄረስ ምስረታ፣ በአንድ በኩል በተለያየ ምሁራዊ እንቅስቃሴ ሲደደገፍና፣ የኋላ ኋላ ደግሞ በኢንዱስትሪ አብዮትና በንግድ አማካይነት መልክ ሲይዝ፣ አስቸጋሪ በሆነባቸው ቦታዎች ኃይል ወሳኝ ሚናን መጫወት ችሏል። በተለይም ከሰላሳኛው ዓ.ም ጦርነት የካቶሊክና የፕሮቴስታንቶች ሃይማኖት ጦርነት በኋላ እ.አ በ1648 ዓ.ም የህብረ-ብሄር ምስረታ ተቀባይነት በማግኘት አብዛኛዎቹ የአውሮፓ አገሮች ብሄራዊ ነፃነታቸውን ለማስከበርና ወደውስጥ ደግሞ መረጋጋትን ለማስፈንና ህዝቡን በአንድ ባንዲራ ስር ለማጠቃለልና የዜጋዊ ስሜትነት እንዲሰማው ለማድረግ ወደ ውስጥ ያተኮረ የተቀነባበረ የኢኮኖሚ ፖሊሲ ግንባታ ማካሄድ ጀመሩ። በየአገሮች ውስጥ የናሺናሊዝም ስሜት በመዳበር ሁሉም አገዛዝ መጀመሪያ አገሬን ታላቅ አገር ማድረግ አለብኝ ብሎ በመነሳት ጥገናዊ ለውጥ ማካሄድ ጀመረ። በዚህም መሰረት ለነጋዴውና በማደግ ላይ ላለው የኢንዱስትሪ ከበርቴ እንክብካቤ በማድረግ የውስጥ ገበያ(Home Market) እንዲስፋፋ ለማድረግ በቃ። ከእንግዲህ ወዲያ ካፒታሊዝምና የህብረ-ብሄረሰብ ግንባታ የማይነጣጠሉ መሰረተ-ሃሳቦች ሆኑ።  ከዚህ ዐይነቱ አጠር መጠን ያለ ትንተና በመነሳት ነው ዛሬ በአገራችን ምድር የተንሰራፋውን አገዛዝና የብሄረሰብ ጥያቄ ጉዳይ መረዳት የምንችለው።

የህብረ-ብሄር ምስረታ ሙከራና የብሔረሰብ ጥያቄ በኢትዮጵያ !

የዛሬይቱ ኢትዮጵያ ግዛት መሰረት የተጣለው ከአክሱም አገዛዝ በፊትና ከአክሱም አገዛዝ ጀምሮ ነው ማለት ይቻላል። ሁላችንም እንድምናውቀው የህብረተሰብ ታሪክ ተከታታይነት ያለውና፣(Evolutionary Process) ከአንድ ቦታ ጀምሮ ወደ ተለያዩ አቅጣጫዎች የሚስፋፋ ነው። የአክሱም ስልጣኔን ልዩ የሚያደርገው ከውጭ በመጣ ባህልና አስተሳሰብ ውስጠ-ኃይል ማግኘት መቻሉ ነው። በመጀመሪያ ግን የግዕዝ ቋንቋን አመሰራረት ስንመለከት፣ ቋንቋው እንደ ፊደል ከመቀረጹና ከማደጉ በፊት የገበሬው የመነጋገሪያ ቋንቋ ነበር። በጊዜው በነበረው ምናልባትም ዳማት በሚባለው ንጉሳዊ አገዛዝ ፊደል ሲቀረጽለት፣ የመጀመሪያዎቹ ፊደሎች ኮንሶናንት ነበሩ። እንደዛሬው የተራቡና በሁለት መቶዎች የሚቆጠሩ አልነበሩም። በአራተኛው ክፍለ-ዘመን የክርስትና ኃይማኖት ሲገባና በንጉስ ኢዛና የሚመራው ንጉሳዊ ቤተሰብ የክርስትናን ሃይማኖት ሲቀበል፣ በዚያው መጠንም የመጀመሪያው የግዕዝ ፊደል ቫውል ተጨምሮለትና ተስፋፍቶ በመነበብ ለቋንቋውና ለባህል ዕድገት ከፍተኛ አስተዋፅዖ ማበርከት ቻለ። ከዚያ በኋላ የያሬድ ሙዚቃና የቤተክርስቲያን የሙዚቃ መሳሪያዎች በመፈጠርና በመዳበር ለባህላዊ ዕድገት ዕምርታ ሊሰጡት ችለዋል። ይሁንና ግን የአክሱም ስልጣኔ በዘጠነኛ ዓ.ም ንግስት ዮዲት ተብላ በምትጠራው የአገው ተወላጅ ሴት ሲደመሰስ የተቀረው ወደ ደቡቡ ክፍል በመሸጋገር እንደገና በአስራሁለተኛው ክፍለ-ዘመን በዛግዌ ዲናስቲ አማካይነት እምርታን በማግኘት ሊያብብ ችሏል። የሰሎሞናዊ ዲናስቲ በመባል የሚታወቀው እስከ አስራአራተኛው ከፍለ-ዘመን ድረስ ስልጣን ከመያዙና ከያዘም በኋላ ግዕዝ የአገዛዞችና የቤተክርስቲያን ቋንቋ ነበር። በሌላ በኩል አማራ እየተባለ የሚጠራው አብዛኛው ህዝብ ደግሞ የሚግባባበት ወይም የመነጋገሪያው ቋንቋው አማርኛ ስለነበር ግራ የተጋባው የንጉሳዊው አገዛዝ የግዕዝን ፊደል በመውሰድና በማሻሻል የአማርኛ ቋንቋ መጻፊያም በማድረግ፣ የንጉሱም ሆነ የተቀረው ህዝብ የመነጋገሪያ ቋንቋ እንዲሆን ያደርጋል። ጨ፣ ሸ፣ ኘ የሚባሉት ፊደሎች በመፈጠርና ከነበረው ፊደል ጋር በመዋሃድ ለአማርኛ ቋንቋ ማደግ እምርታን ይሰጡታል።

ይህ በእደዚህ እንዳለ የሰለሞናዊት አገዛዝ ፊዩዳላዊ የመሬት ስሪትን በማስፋፋት በገባርና በአስገባሪዎች መሀከል ያለውን ግኑኝነት ያጠነክራል። የክርስቲያኑ ገበሬ ርስት የሚባል የመሬት ይዞታ ቢያገኝም ለፊዩዳሉ መደብ፣ ለንጉሳዊ ቤተሰቦችና ለቤተክርስቲያን ግብር በመክፈል የሚበዘበዝ ነበር። ከዚህም በላይ የአብዛኛው ህዝብ ሙያ ግብርና ስለነበርና፣  በዕደ-ጥበብ ሙያ ከተሰማራው ጥቂቱ የህብረተሰብ ክፍል ጋር የመገናኘትና የመገበያየት ዕድል ስላልነበረው ምርታማነትን በማሻሻልና የተወሰነውን ምርቱን ገበያ አውጥቶ በመሸጥ ኑሮውን ማሻሻል አልቻለም። ከሰለሞናዊ አገዛዝ በኩል የአስተዳደር ጥገናዊ ለውጥና ከውጭ የመጣ ሃይማኖትን ለመቀበል የተደረገው ሙከራ በመክሸፉ የፊዩዳሉ ስርዓት ለብዙ መቶ ዓመታ እንዲቆይ አድርጎታል። ይሁንና ግን ንጉሳዊው አገዛዝ ሌሎች ከሱ ክልል ውጭ ያሉትን በማስገበር ተገዢ ለማድረግ ችሏል። በአንድ ግዛት ስር ባልተጠቃለሉ፣ ይሁንና ግን ግብር እንዲከፍሉ በተደረጉ የደቡብ ግዛትም ዘንድ የሰራ-ክፍፍልና የንግድ እንቅስቃሴ ለመዳበር ባለመቻላቸው እነሱም በዕድገት ወደ ኋላ የቀሩና የኋላ ኋላ በመጀመሪያ በክርስትና ሃይማኖት መስፋፋት ወደ አንድ ግዛት ለመጠቃለል ያመሩ ክፍሎች ነበሩ ማለት ይቻላል። የማዕከላዊ ግዛት መሰረት ሊሆኑ የሚችሉ ነገሮች በጣም በውስን ደረጃ የተጣሉት በአፄ ቴዎድሮስ አማካይነት ሲሆኑ፣ ኢትዮጵያን ዘመናዊና የኢንዱስትሪ አብዮት ዕድል እንዲያጋጥማት ለማድረግ ያላቸው ህልም፣ ከውስጥ በፊዩዳሉ የገዢ መደቦችና መሳፍንቶች፣ እንዲሁም የሃይማኖት መሪዎች፣ ከውጭ ደግሞ በተለይም በእንግሊዞች ተንኮል ይጨናገፋል። አፄ ቴዎድሮስ እንግሊዞችን ኢንጂነሮችንና በተለያዩ ሙያዎች የሰለጠኑ ሰዎችን እንዲልኩላቸው ደብዳቤ ሲጽፉ፣ እንግሊዞች የላኩላቸው ግን የሃይማኖት ሰባኪ ቄሶችን ነው። የዚህ ውጤት ምን እንደሆነ ይታወቃል። ያም ሆነ ይህ  አፄ ቴዎድሮስ ካለጥገናዊ ለውጥና ካለ ኢንዱስትሪ ወይም ቴክኖሎጂያዊ ምጥቀት ህብረ-ብሄር እንደማይመሰረት ገብቷቸው ነበር ማለት ይቻላል። ይህ ህልማቸው ግን የኋላ ኋላ በአፄ ምኒልክ እስከተወሰነ ደረጃ ድረስ ተግባራዊ ሊሆን በቅቷል።

አንዳንድ የአሮሞ ምሁራን የአፄ ምኒልክን ወደ ደቡቡ ክፍል መስፋፋትንና ሌሎችን አካባቢዎች በአንድ አገዛዝ ስር ማጠቃለል ልዩ አድርገው ይመለከቱታል። በሌላ አነጋገር በነሱ ግምት እንደዚህ ዐይነቱ የተቀረውን አካባቢ በአንድ አገዛዝ ስር በኃይል ማጠቃለል በኢትዮጵያ ምድር ብቻ እንደተካሄደ አድረገው ነው የሚያቀርቡት፤ ወይም ሰውን ለማሳመን የሚሞክሩት። ይህ ግምታቸው ወይም ታሪክን በዚህ መልክ መተርጎማቸው በዓለም አቀፍ ደረጃ ህብረ-ብሔረን ለመመስረት ከተደረገው ሙከራና ከተሳካው ጋር በፍጹም የሚጣጥም አይደለም። በመጀመሪያ ደረጃ በአፄ ምኒልክ የአገዛዝ መዋቅር ውስጥ አማራዎች ብቻ ሳይሆኑ፣ ራሳቸው የኦሮሞ የገዢ መደቦችም ተሳትፈውበታል። በሌላ አነጋገር የተገለጸላቸው የኦሮሞ የገዢ መደቦች የህብረ-ብሄርን ምሰረታ የደገፉና የጦር አዝማቾችም ነበሩ። በእርግጥ የአፄ ምኒልክ ወታደሮች አልገበር ያሏቸውን ባላባቶች አንዳንድ አላስፈላጊ የሆኑ እርምጃዎች ወስደውባቸዋል። እንደዚሁም የኦርሞ ተዋጊዎች በአፄ ምኒልክ ወታደሮች ላይ ከፍተኛ እልቂት አስከትለዋል። የታሪክ ማስረጃዎች እንደሚያረጋግጡት ከሆነ በሁለቱም በኩል ብዙ ሰው ህይወቱን አጥቷል።፡

በአብዛኛዎቹ የኦሮሞ ኤሊቶች የታሪክ አተረጋጎምና ግንዛቤ መሰረት ኦሮሞዎች በአንድ አገዛዝ ስር የሚታደደር ማህበረሰብ እንደነበራቸው ሆኖ ነው የሚቀርበው። እንደሚታወቀው ኦሮሞዎች ዛሬ ኦሮሚያ የሚባለውን ግዛት ከመቆጣጠራቸው በፊት ግዛቶቹ በአምስት የተለያዩ ብሄረሰቦች ቁጥጥር ስር የነበሩና ነገስታትም የሚተዳደሩ ነበሩ። እነዚህ ነገስታትና ብሄረሶቦቻቸው በእርሻ ሙያና በሌሎች ነገሮች የሚተዳደሩ ነበሩ። ከአስራስድሰተኛው ክፍለ-ዘመን ጀምሮ ኦሮሞዎች ወደ ተለያየው የኢትዮጵያ ክፍላተ-ግዛት ሲስፋፉ እነዚህን ነገስታት በመደምሰስ ነው ብዙ ቦታዎችን መቆጣጠር የቻሉት። ወደ አማራው ክፍላተ-ግዛትም በመስፋፋትና ከህዝቡ ጋር በመጋባትና በመዋለድ በዚያ አካባቢ በልዩ ልዩ መልክ ለሚገለጸው የባህል ዕድገት አስተዋፅዖ አበርክተዋል። የኦሮሞ ኤሊቶችን ታሪክ ለመቀበል የሚያስቸግረው ሌላው ምክንያት አቀራረባበቸው ከህብረተሰብና ከህብር-ብሄር አገነባብ ታሪክና ሂደት ጋር በፍጹም ስለማይጣጣም ነው። በሌላ አነጋገር፣ የኦሮሞ ብሄረሰብ እንደ አንድ ህብረ-ብሄር በአንድ ማዕከላዊ አገዛዝ ጥላ ስር ተደራጅቶ የነበረ አይደለም። ለአንድ ማዕከላዊ አገዛዝና ህብረ-ብሄር የሚያስፈልጉ ቅድመ-ሁኔታዎች የኦሮሞ ኤሊቶች ኦሮሚያ ብለው በሚጠሩት አካባቢና ማህበረሰብ ውስጥ አልነበረም። በቋሚ ወታደር፣ ፖሊስና በሲቪል ቢሮክራሲ የተደገፈ የአስተዳደር መዋቅር በየቦታው አልነበራቸውም። እንደዚሁም ህዝቡን ለማስተዳደር የሚያስችል በየቦታው የተዘረጋ ኢንስቲቱሽን አልነበራቸውም። ከዚህም በላይ ለአንድ ህብረ-ብሄር እንደ መሰረታዊ ቅድመ-ሁኔታ የሚያስፈልግ በማኑፋክቱር ላይ የተገነባ ኢንዱስትሪና ሰፋ ያለና የዳበረ የስራ ክፍፍል አልነበራቸውም። በተጨማሪም ሰፋ ያለ የገበያ ኢኮኖሚ አልነበራቸውም። ከዚህና ከሌሎች ለአንድ ህብረ-ብሄር ከሚያስፈለጉ መሰረታዊ ጉዳዮች ስንነሳ ኦሮሞን እንደ ብሄር ወይንም እንደ ህብረ-ብሄር የሚያስጠራው ምንም ዐይነት ሳይንሳዊ ማስረጃ የለም። ስለሆነም በሌለ ነገር ላይ መነታረኩ ጊዜ ማጥፋት ነው የሚሆነው። የጋራ ችግርንም በአንድነት ተሰማምቶና ተባብሮ እንዳንሰራ እንቅፋት ይሆናል። ለሁለመንታዊ ዕድገት በሆኑ የሳይንስ፣ የቴክኖሎጂና የፍልስፍና ጉዳዮች ላይ እንዳንረባረቡ መንገዱን ይዘጋብናል።

ያም ሆነ ይህ የአፄ ምኒልክ አገዛዝ ወደ ደቡቡ ክፍል መስፋፋትና፣ እዚያ አዳዲስ የአስተዳደር መዋቅሮችን መዘርጋት አዲስ የህብረተሰብ ግኑኝነት(Social and political relationship) እንደፈጠረ መገንዘብ ይቻላል። በማዋቅም ሆነ ባለማወቅ በባላባትና በጭሰኞች መሀከል የሚገለጽ ግኑኝነት ሊፈጠር ተችሏል። በዚህ ዐይነቱ አዲስ የህብረተሰብ ግኑኝነት የአፄ ምኒልክን አገዛዝ የተቀበሉ የየአካባቢው ባላባቶችም ተጠቃሚ ሆነዋል። ይህም ማለት የባላባትና የጭሰኝነት ግኑኝነት በመጤው አማራና በኗሪው ህዝብ ብቻ የሚገለጽ አልነበረም። የዚህ ዐይነቱን አጠቃላይ የፊዩዳል ስልተ-ምርት ግኑኝነት መረዳት የሚቻለው በዘመኑ የነበረውን የፖለቲካ፣ የህብረተሰብ፣ የባህልና የኢኮኖሚ ንቃታ-ህሊና መዳበርና አለመዳበር ጋር ያገናኘን እንደሆን ብቻ ነው። እንደሚታወቀው አፄ ምኒልክ የተገለጸለት አዲስ ቢሮክራሲያዊና ምሁራዊ መሰረት አልነበራቸውም። የአስተዳደራቸው መሰረት የፊዩዳል ኢንስቲቱሽንና ቤተክርስቲያን ነበሩ። እሳቸው በአስተሳሰብ በብዙ እጅ ቀድመው የሄዱ ቢሆንም የሳቸውን የዘመናዊነት ፍላጎትና ህልም በምሁራዊ ዘዴ እየተነተነ ተግባራዊ የሚያደርግ ኃይል ባለመኖሩ የዘመናዊነቱ ሂደት ውስንና ውስጠ-ኃይሉም በጣም ደካማ ነበር። ይሁንና ግን አንድ ኢትዮጵያን ለመመስረት የሚያስችልና፣ ዛሬ ኢትዮጵያ ብለን ለምንጠራትና የራሳችንም መለያ ለመሆን የበቃች እገር መሰረት ጥለው አልፈዋል ማለት ይቻላላል።

በአጠቃላይ ሲታይ የኢትዮጵያን ወደ ህብረ-ብሄር መሽጋገርና በጠንካራ መሰረት ላይ እንድተገነባ አስቸጋሪ የሚያደርገው ነገር የተለያዩ የአገሪቱ ግዛቶችች፣ ከተማዎችና መንደሮች በስነ-ስርዓት አለመገንባታቸው፣ የዕደጥበብ ሙያና የንግድ እንቅስቃሴ አለማደጋቸው፣ በዚህም አማካይነት ከክልላዊ አስተሳሰብ ተላቆ በሰፊ ሜዳ ላይ ለመዋኘት የሚፈልግ የከበርቴ መደብ መፍለቅ አለመቻሉ ነው። ይህ ዐይነቱ የተጨናገፈ አካሄድ የኋላ ኋላ በብሄረሰብ ደረጃ ለሚንቀሳቀሱ፣ የታሪክን ሂደትና የህብረተሰብ ግንባታን ለመረዳት ለማይፈልጉ ኃይሎች መንገዱን አመቻችቷል ማለት ይቻላል።

ያልተስተካከለ ዕድገት፣(Unequal Development)የብሔረሰብ ጥያቄ አነሳስና

ጎልቶ መታየት !

አፄ ምኒልክ ከሞቱ በኋላ አፄ ኃይለስላሴ ከስደት እስኪመለሱ ድረስ ያለውን ጊዜ በመተው፣ ንጉሱ እንደገና የስልጣን ወንበራቸው ላይ ከተቀመጡ በኋላ የተከተሉትን ፖለቲካና የኢኮኖሚ ፖሊሲ ጠጋን ብለን እንመልከት። በአፄ ኃይለስላሴ ዘመን የማዕከላዊ አገዛዝ ሂደት እንደተጠናቀቀ ይታወቃል። ይሁንና ግን አፄ ኃይለስላሴ እንደገና ስልጣናቸውን ከተረከቡ በኋላ የሰሩት ትልቅ ስህተት የጣሊያን ወራሪ ኃይል የደመሰሰውን የፊዩዳል ስርዓት እንደገና መመለሳቸውና ማጠናከራቸው ነው። በተጨማሪም ጣሊያን ያቋቋማቸውን አዳዲስ ኢንስቲቱሽኖችና የገነባቸውን ከተማዎች በዚያው በመቀጠል ከማስፋፋትና ከማዳበር ይልቅ እንዲፈራርሱ ማድረጋቸው ነው። በእሳቸው ዘመን አዲስ አበባ ውስጥ አዲስ ቢሮክራሲያዊ ኃይል ቢቋቋምም ወደ ክፍለ-ሀገር ከተማዎችና ወረዳዎች፣ እንዲሁም ምክትል ወረዳዎች ስንሄድ አፄ ኃይለስላሴ የዘረጉት የተገለጸለት ዘመናዊ ኢንስቲቱሽን አልነበረም። በመሆኑም የአገሪቱን የሰውና የማቴሪያል ሀብት ሊያንቀሳቅስና ህዝባዊ ሀብት ሊያዳብር የሚችል ዘመናዊ እንስቲቱሽን አልነበረም። ስለሆነም ግራ የተጋባውና ያልተማረው ህዝብ የተሰማራው እስከዚህም ድረስ ሀብረተሰብአዊና ብሄራዊ ሀብት(National and Social Wealth) ሊፈጥሩ በማይችሉ ጥቃቅን የኢኮኖሚ ዘርፎች ላይ ነው። በመሰረቱ እነዚህ ከእጅ ወደ አፍ የማያልፉ የገቢ ምንጮች በመሆናቸው በየሎካሉ ላሉ ኋላ-ቀር አስተደዳሮች የገቢ ቀረጥ ምንጮች ሊሆኑ የቻሉ አልነበሩም። በዚህም ምክንያት የተነሳ የየሎካሉ አስተዳደሮች በቂ የገቢ ምንጭ ስላለነበራቸው ለህዝቡ የሚያገለግሉ ልዩ ልዩ ፕሮጀክቶችንና የስራ መስኮችን ሊያቋቋሙም ሆነ ሊከፍቱ አልቻሉም። በጊዜው የነበሩትም የሎካል የአስተዳደር መዋቅሮች እጅግ ወደ ኋላ የቀሩ በመሆናቸው እንዴት አድርገው አካባቢያቸውን ማልማት እንደነበረባቸው እስከዚህም ድረስ የሚያውቁት ነገር የለም። አብዛኛው ስራ የሚሰራው በዘፈቀደ ነበር ማለት ይቻላል።

ወደ አጠቃላዩ የኢኮኖሚ ፖሊሲያቸው ስንመጣ ደግሞ በማወቅም ሆነ ባለማወቅ አፄ ኃይለስላሴ የተከተሉት የኢኮኖሚ ፖሊሲ በዘመኑ በሌሎችም የሶስተኛው ዓለም አገሮች የተካሄደውን ዐይነት የምትክ የኢንዱስትሪ ተከላ( Import Substitution  Industrialization) እየተባለ የሚጠራውን ነው። እንደሚታወቀው ጣሊያን ጠቅላላ አገሪቱን ሲገዛ ለራሱ ፍጆታ የሚጠቅም ኢንዱስትሪዎች አስፋፍቶ ነበር። እንዲሁም የሬዲዮ ጣቢያ ዘርግት ነበር። አፄ ኃይለስላሴ እንደገና ስልጣናቸውን ሲረከቡ በሞግዚትነት ተከትላቸው የመጣችው እንግሊዝ ጣሊያን ያቋቋመውን ኢንዱስትሪና የሬድዮ ጣቢያ ነቃቅላ በመወሰድ አገዛዙ ሀ ብሎ እንዲጀምርና ሁኔታውን እንዲያዘበራርቅ አድርጋለች። ያም ሆነ ይህ አፄ ኃይለስላሴ ስልጣን ከተረከቡ በኋላ በአዲስ አበባና በአካባቢው፣ እንዲሁም በአንዳንድ የክፍለ-ሀገር ከተማዎች ያቋቋሟቸው ኢንዱስትሪዎች ለአጠቃላይ የሀብት ክምችት( Capital Accumulation)  የሚያገለግሉና በየአቅጣጫው ሊስፋፉ የሚችሉ አልነበሩም። ሰፋ ያለ በሁሉም መልክ ሊገለጽ የሚችል ለስራ-ክፍፍል መዳበር የሚያመች የኢንዱስትሪ ፖሊሲ አይደለም አፄውና አገዛዛቸው የተከተሉት። እነዚህም የስኳር፣ የብስኩት፣ የመጠጥ፣ የጨርቃ ጨርቅ፣ የሲጋራና፣ እነዚህን የመሳሰሉትን የኢንዱስትሪ ተከላዎችን ነው የአፄው አገዛዝ ተግባራዊ ያደረገው። እነዚህ ኢንዱስትሪዎች በአዲስ አበባና በአካባቢው በመቋቋመቸው፣ 1ኛ) የሰው ኃይል ፍልሰት ከገጠር ወደ አዲስ አበባ እንዲያመራና ከተማዋን እንዲያጣብብ አድርጎታል። 2ኛ) የአዲስ አበባ ከተማ ራሱ በእቅድ የተሰራ ስላልነበር አዳዲስ የሰው ኃይል ከገጠር ሲመጣ ይህን አዲስ የህብረተሰብ ክፍል ሊያስተናግድና መጠለያ ሊሰጥ የሚችል ኢንስቲቱሽን አልነበረም። በመሆኑም ህዝቡ ራሱ በዘፈቀደ እዚህና እዚያ አልባሌ መኖሪያቤቶችን  በመስራትም ሆነ በመከራየት አዲስ አበባ በዕቅድና ስርዓት ባለው መልክ እንዳትገነባ ለመሆን በቃች። 3ኛ) ከገጠር ወደ አዲስ አበባ የዘመተው አዲስ የሰው ኃይል ዘመናዊ በሚባሉ የኢኮኖሚ መስኮች ውስጥ የስራ ዕድል ለማግኘት ባለመቻሉ ባልባሌና ሀብትን ሊፈጥሩ በማይችሉ የስራ መስኮች እንዲሰማራ ተገደደ። ሴቱ፣ ሴተኛ አዳሪ፣ እንጀራ ጋጋሪና በችርቻሮ የሚተዳደር ሲሆን፣ ወንዱ ደግሞ በሊስትሮነት፣ በሱቅ ነጋዴነትና፣ በአናጢነትና በልብስ ስፌትነትና እነዚህን በመሳሰሉት፣ ኢንፎርማል ሴክተር በመባል በሚታወቁት እንዲተዳደር ተገደደ። 4ኛ) ይህ ዐይነቱ ኢንፎርማል ሴክትር ዘመናዊ ከሚባለው የኢኮኖሚ መስክ ጋር ግኑኝነት ስላልነበረው፣(Linkages) ህብረተሰብአዊና ብሄራዊ ሀብት ለመፍጠር የሚያስችል አልነበረም። በዚህ መስክ ተሰማርቶ የሚተዳደረው የህብረተሰብ ክፍል ገቢው በጣም ዝቅተኛ በመሆኑ ከዘመናዊ መስክ የሚመረቱትን ምርቶች ገዝቶ ለመጠቀም አይችልም ነበር። 5ኛ) ይህ ዐይነቱ ግኑኝነት አለመኖርና የሰፊውም ህዝብ የመግዛት ኃይል መዳከም፣ በአንድ በኩል የገንዘብን በፍጥነት መሽከርከር ሲያግደው፣ በሌላው ወገን ደግሞ ለአገዛዙ ሰፊ የገቢ ቀረጥ መሰረት ሊጥልለት አልቻለም። በዚህም ምክንያትና አገዛዙ በተከተለው የተበላሽና የህብረተሰቡን ፍላጎት ያላካተተና ቀስ በቀስ ከታች ወደ ላይ ሊያድግ የሚችል የኢንዱስትሪ ተከላና ኢኮኖሚያዊ ዕድገት( Systematic Industrialization and Organic Growth) ባለመከተሉ በአገሪቱ ውስጥ ያልተስተካከለ ዕድገት(Unequal Development) ሊስፋፋ ችሏላ። ይህ ዐይነቱ የተበላሸ የኢኮኖሚ ፖሊሲ ትንሽ ገንዘብ ያለውን ባለሀብት ወደ ነጋዴነት እንዲያመራና እንዲያተኩር በማድረግ በአገሪቱ ምድር በኢንዱስትሪ ተከላ ላይ ሊያተኩርና ቀስ በቀስ እያለ ሊያድግ የሚችል የኢንዱስትሪ ከበርቴ እንዳያድግ አደረገ። በተጨማሪም ይህ ዐይነቱ የተዘበራረቀና ዓላማው ምን እንደሆን የማይታወቅ የኢኮኖሚ ፖሊሲ አስተሳሰቡ የተዘበራረቀበት የህብረተሰብ ክፍል እንደአሸን እንዲፈልቅ አደረገ። ከኢትጵያዊነት ይልቅ አሜሪካንን የሚናፍቅ ኃይልና፣ ከዘጠና በመቶ በላይ ከሚሆነው ህዝብ የተገለለና በራሱ ዓለም ውስጥ የሚኖር የህብረተሰብ ክፍል ብቅ በማለት ባህላዊና ማህበራዊ ቀውስ እንዲፈጠር ተደረገ። በዚህም መሰረት የኢኮኖሚው ፖሊሲ በአገሪቱ ውስጥ ሰፋ ያለና ዘመናዊ ገበያ እንዲዳብርና እንዲስፋፋ የማያመች በመሆኑ ህብረተሰቡን ሊያስተሳስር፣ የማሰብ ኃይሉን ሊያዳባር የሚያስችለው፣ የፈጠራ ችሎታውን ሊያሳድግና አዳዲስ መሳሪያዎችንና ምርቶችን  በማምረት ማንነቱን ሊገልጽ የሚችል የህብረተሰብ ክፍል ብቅ ሊል አልቻለም። በአፄው ዘመን ሰፊው የኢትዮጵያ ህዝብ እንደ ነፃ ዜጋ የሚታይና መብትና ክብር ያለው መሆኑ የሚቆጠርና የሚከበር አልነበረም። ዘመናዊ የሚባለው አዲስ አበባ የተዘረጋው ቢሮክራሲ ይህንን ክፍተትና ኋላ-ቀርነት ለማረም የሚችል ባለመሆኑ፣ በአገሪቱ ውስጥ እዚያው በዚያው ዘመናዊና ፊዩዳላዊ የአስተዳደር መዋቅሮች በመዘርጋት ለአጠቃላይ ዕድገት ጠንቅ መሆን ችለዋል ማለት ይቻላል። በመሆኑም የአፄው አገዛዝ ፖለቲካዊ፣ ህብረተሰብአዊ፣ ባህላዊ፣ ኢኮኖሚያዊ ንቃተ-ህሊና የጎደለው ብቻ ሳይሆን፣ ስትራቴጂካሊ ለማሰብ የሚችል አልነበረም። በአገሪቱ ውስጥ ሰላም እንዲስፈንና አገሪቱም በውጭ ኃይሎች እንዳትጠቃ በኢኮኖሚ መስክ መካሄድና መወሰድ ያለበትን ሁለ-ገብ የኢኮኖሚ ፖሊሲ ተግባራዊ ለማድረግ ባለመቻሉ ለሰላም ጠንቅ የሆኑ ነገሮችን ዘርግቶ አለፈ።

ወደ መንግስት መኪናው አውቃቀር ስንመጣ፣ መንግስታዊው አወቃቀር ከታች ወደላይ ከህብረተሰቡ የማቴሪያል ዕድገት ጋር እየተቀናጀ ያደገ መንግስታዊ አወቃቀር አይደለም የተዘረጋው። የወታደሩ፣ የፀጥታው ኃይል፣ ፖሊስና ሌሎች አውታሮችም በውጭ ኃይሎች የሰለጠኑ በመሆናቸው ለውጭ የስለላ ኃይል ሰርጎ መግባት የሚያመቹ ነበሩ። ይህ ዐይነቱ ስርጎ መግባት በተለይም አብዮቱ ከፈነዳ በኋላ ተግባራዊ የሆነና፣ በወታደሩና በፀጥታው ኃይል መተማመን እንዳይፈጠር ያደረገ ነው። አሜሪካንን በሚደግፍና መረጃዎችን የሚያቀብል፣ በሌላ ወገን ደግሞ ቀስ በቀስ እያለ ለሶቭየቶች ታማኝ ሊሆን የሚችል ኃይል የሚመለመልበት ነው። ይሁንና ግን የኢትዮጵያ መንግስት መኪና አወቃቀር  ለብዙ ዐመታት ከአሜሪካኖች ጋር የተያያዘ ስለነበርና፣ የአሜሪካን የኑሮ ፍልስፍና ከደሙ ጋር የተዋሃደ ስለነበር፣ በተለይም ኮሙኒዝምን ወይም ሶሻሊዝምን የሚጠላው ኃይል ለአሜሪካ ያደላና በአብዮቱ ዘመን ህብረተሰብአዊ ለውጥ እንዳይኖር ያገደ ነው። ይህ ኃይል ደርግ ሊወድቅ ሲልና በኋላ የአሜሪካን ፓስፖርት እየተሰጠው አሜሪካን ገብቶ ኑሮውን እንዲመሰርትና ተደላድሎ እንዲኖር የተደረገ ነው።

ያም ሆነ በታሪክ ውስጥ የመንግስትን አመሰራረትና ለዕድገት አመቺ መሆን አለመሆን ስንመለከት በራሳቸው ጥረት የመንግስታቸውን መኪና ያላዋቀሩ አገሮችና የራሳቸው ፍልስፍናዊ መመሪያ የሌላቸው አገሮች ለዕድገት ጠንቅ እንደሚሆኑ ነው።  የሶቭየቱና የቻይናው አብዮት ከሞላ ጎደል ሊሳካና እነዚህ አገሮች ኃያልና የሚፈሩ መንግስታት ሆነው ብቅ ማለት የቻሉት የራሳቸውን የመንግስት መኪና በራሳቸው ጥረት በመገንባታቸው ብቻ ነው። ይህ ዐይነቱ በራስ ጥረት የመንግስት መኪናን ማዋቀርና አገርን መገንባት አገር ወዳድነትንና ብሄራዊ ስሜትን ያዳብራል።ለዕድገት ያመቻል። መተማመንን ይፈጥራል። በህዝብና በአገዛዝ መሀከል ሊኖር የሚገባውን መደጋገፍና መተሳሰብ ያጠናክራል። ዛሬ በብዙ የሶስተኛው ዓለም አገሮች፣ በተለይም በአፍሪካ አገሮች ውስጥ ያለውን ጭቆና፣ የሀብት ዘረፋና ሙስና ስንመለከት ዋናው ምክንያት መንግስታትና አገዛዞች ከታች ወደ ላይ በአንዳች ፍልስፍናና ሳይንስ ያልተገነቡ መሆናቸውን ናቸው። አብዛኛዎቹ መንግስታት በውጭ ኃይሎች በተለይም በአሜሪካን ኢምፔሪያሊዝም የሚጠመዘዙና የእሱንም ጥቅም የሚያስጠብቁ ናቸው። ስለሆነም በአንዳች ፍልስፋና የማይመሩና የህዝቦቻቸው ተጠሪ ያልሆኑ አገዛዞችና መንግስታት በብዙ ሚሊዮን የሚቆጠር ህዝብ ላይ ስቃይን ያደርሳሉ፤ አንድ አገር በዘለዓለማዊ ትርምስ ውስጥ እንዲኖር ያደርጋሉ። ችግሩ ከአንድ ትውልድ ወደ ሌላ እንዲሸጋገር በማድረግ ህዝቦች በዘለዓለማዊ ድህነት ውስጥ እንዲኖሩ ያደርጋሉ።  ህዝባቸው በራሱ ላይ እንዳይተማመንና ቢያንስ እንኳ መሰረታዊ ነገሮችን እንዳያሟላ እንቅፋቶችን ይፈጥራሉ። ስለዚህም ለአገር ወዳድነትና ብሄራዊ ስሜት መዳበር በአዲስ ፍልስፍና ላይ የተመሰረተ የመንግስት መኪና አወቃቀር እጅግ አስፈላጊ መሆኑን መረዳት ያስፈልጋል። አዲሱ የመንግስት መኪናና ልዩ ልዩ ኢንስቲቱሽኖችም ከማኝኛውም የውጭ ኃይል ተፅዕኖ የተላቀቁ መሆን አለባቸው። ከላይ እስከታች ያሉ ባለስልጣናትም ሆነ አዳዲስ የሚቀጠሩ ወይም የሚሾሙ የህይወት ታሪካቸው መጠናት አለበት። ቀደም ብሎ ሆነ አሁንም ከማንኛውም የውጭ ኃይል ጋር በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ግኑኝነት የነበረውና የውጭ ኃይሎችን የሚያመልክ ግለሰበም ሆን ቡድን ለስልጣን እንዲበቃ መደረግ የለበትም፤ ወይም በአማካሪነትም ቢሆን እንኳ በስልጣን አካባቢ መድረስ የለበትም። ይህ ሲሆን ብቻ ነው አንድ አገር በሁሉም አቅጣጫ ለማደግና ህዝቦቿም ዕውነተኛ ነፃነትን ሊቀዳጁ የሚችሉት። ይህንን የተቀደሰ ዓላማ በሆነው ባልሆነው ለማሰናከል መሞከርና የማይሆን ዘመቻ እያካሄዱ እንቅፋት መፍጠር የኢዮጵያዊነትን ስሜት ማኮላሸቱ ብቻ ሳይሆን ህዝባችን ዘለዓለሙን ደሀ ሆኖ እንዲቆይ ሁኔታውን ማመቻቸት ነው። በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ በሳይንስና በቴክኖሎጂ ላይ የተመሰረተ ጠንካራ አገር እንዳይገነባ እንደማሰናከል ይቆጠራል። ዛሬ በአብዛኛው ተማርኩ በሚለውና ውጭ አገር በሚኖረው ምሁር ዘንድ ያለው ትልቁ ችግርና የአስተሳሰብ ክፍተት ይህንን ሁኔታ በቅጡ ለመረዳት አለመቻል ነው። በተጨማሪም ለውይይትና ለክርክር ዝግጁ ባለመሆን ሽምጥጥ በማለት ወደ ስልጣን ለማምራት ከፍተኛ ሩጫ ማድረግ የትኛው አገር ወዳድ እንድሆነ የትኛው ደግሞ የአገር ጠላት እንደሆነ ለማወቅ የማይቻልበት ሁኔታ ተፈጥሯል።

የብሄረሰቦች እንቅስቃሴ መጠንሰስና መስፋፋት፣ እንዲሁም ብሄራዊ ስሜት ያለመዳበር ጉዳይ !

የኤርትራን የነፃ አውጭ ድርጅቶች መጠንሰስ ስንመለከት በመሰረቱ የኢጣሊያን የቅኝ አገዛዝ ያሰፈነው ልዩ ዐይነት ስርዓት በተወሰነው የኤርትራ የህብረተሰብ ክፍል ላይ የህሊና ጫና ወይንም ደግሞ የኢትዮጵያዊነት ስሜት እንዳይዳብር አድርጎታል። በተጨማሪም የአረቦች ተፅዕኖ ቀስ በቀስ ነፃ አውጭ ነኝ የሚሉትን በኢትዮጵያና በኢትዮጵያዊነት ላይ ዘመቻ እንዲያካሂዱ አግዞአቸዋል። በተለይም አፄው ኤርትራን ለጊዜው በፌዴሬሽን መተዳደርና፣ ጊዜው ከማለቁ በፊት በኃይል ማጠቃለል ኤርትራው ውስጥ የነበረውን ሁኔታ የባሰውን አባብሶታል። አፄው ስትራቴጂካል በሆነ መልክ ማሰብ የማይችሉ በመሆናቸውና የሪፐብሊክ አሰተሳሰብ የተዋሃዳቸው ስላልነበሩ በኤርትራም ሆነ በጠቅላላው የአገሪቱ ግዛት ፓርሊሜንተሪ ዲሞክራሲ እንዲዳብር ለመፍቀድና ሁኔታውን ለተረጋጋና ለዕድገት ለማመቻቸት ዝግጁ አልነበሩም። የመሰላቸው በሽወዳና በተንኮል እንዲሁም በኃይል ሁኔታውን መቆጣጠር የሚችሉ ሆኖ ነው የተሰማቸው። የዲስፖቲክ አገዛዝ ዋናው ችግር  ኃይል አለኝ ብሎ ስለሚገምትና ሁሉንም ለመቆጣጠር የሚችል ስለሚመስለው አንድን የፖለቲካ ክስተት ከሁሉም አቅጣጫ ለማየት አለመቻሉ ብቻ ሳይሆን፣ አማካሪው የሚለውን ባለመስማትና በጥርጣሬ ዐይን በመመልከት ያለውን ሁኔታ የባሰውን ማባባስ ነው። ስለሆነም አፄ ኃይለስላሴ የተከተሉት ስታሬቴጂክና ፖለቲካ አልባ አካሄድ የኤርትራን ነፃ አውጭ ድርጅቶች እልክ ውስጥ ከተታቸው። አብዮቱ ከፈነዳም በኋላና እስከመጨረሻው ድረስ የተካሄደው በእልክ ላይ የተመሰረተ የጭፍጨፋ ፖለቲካ ሁኔታው የባሰውን አበላሸው እንጂ ለችግሩ መፍትሄ ሊሆን በፍጹም ሊሆን አልቻለም። በሰፊው ሳይታሰብበትና ከሁሉም አቅጣጫ ውይይት ሳይካሄድበት ዝም ብሎ በፊዩዳል ግብዝነት „ሁሉንም ነገር ወደ ጦር ግንባር“ በሚለው መፈክር የተደረገው ዘመቻና ጦርነት የሰውና የማቴሪያል ኃይል የፈሰሰበት፣ የአገሪቱን ሁለ-ገብ ዕደገትና የኢትዮጵያዊነትን ስሜት እንዲቦረቦር ያደረገ ነው። ማንም ኃይል አንድን የህብረተሰብ ክፍልም ሆነ የብሄረሰብ እንቅስቃሴን በጉልበት ሊያሸንፈው አይችልም። ውስጥ ካለው የተዛባ የፖለቲካ፣ የማህበራዊና የኢኮኖሚ ፖሊሲ ጋር ተያይዞ የሚያድግ እንቅስቃሴ በመሆኑ፣ እንደዚህ ዐይነቱን የውስጥ ችግር በፖለቲካ ሪፎርምና ሁለ-ገብ በሆነ የኢኮኖሚና የማህበራዊ ግንባታ ፖሊሲ ብቻ ነው ማረምና ብሄራዊ ወይም የአገር ወዳድ ስሜትነት ማዳበር የሚቻለው።

በሌላ ወግን ግን የኤርትራው የነፃ መውጣት እንቅስቃሴ ብሶት የወለደውና የቅኝ አገዛዝ የህሊና ተጽዕኖ ውጤት ቢሆንም፣ እንቅስቃሴው የተጀመረውና የተካሄደው በተገለጸላቸውና የዲሞክራሲን ትርጉም በተረዱና ከጭንቅላታቸው ወይም ከሰውነታቸው ጋር ባዋሃዱ ኃይሎች አይደለም። እንቅስቃሴው እየጎለመሰ ሲሄድ ወደ ዘረኝነትና ወደ ማንአለኝበት ያመራና፣ በእንቅስቃሴው ውስጥም የትግሉን ዓላማ ለመወያየት ለዲሞክራሲያዊ ውይይት የሚያመች ሁኔታ የሌለበት ወደ አምባገነንነት ያመራ ነው። ስለሆነም ወጣቱ ክፉውን ከደጉ እንዳይለይ በጥላቻና በንቀት መንፈስ እንደሚረዝ በማድረግ፣ ከምሁራዊ እንቅስቃሴ ይልቅ ይበልጥ ወደ ጦርነት ስልትና ትግል በማምራት ጭካኔነትን ከደሙ ጋር እንዲያዋህድ ለማድረግ በቃ። በጦርነቱ ውስጥ የተሳተፉትና ከሞት የተረፉት የኢትዮጵያ ወታደሮች እንደመዘገቡት ከሆነ በተማረኩት የኢትዮጵያ ወታደሮች ላይ ይደርስ የነበረው ስቃይ እጅግ ዘግናኝ እንደነበር ነው። ይህ ብቻ አይደለም። አቶ ኢሳያስና ግብረ አበሮቹ ኤርትራን ከኢትዮጵያ ለመገንጠልና ነፃ ለመውጣት ሲሉ አዲስ አበባና አንዳንድ የአገሪቱ የክፍለሀገር ከተማዎች በንግድና በስራ ዓለም ተሰማርተውና ተደላድለው፣ እንዲሁም ሀብት አፍርተው የሚኖሩ ኤርትራውያንን ሁሉ በጥላቻ መንፈስ በመመረዝና ማፊያዊ በሆነ መልክ በማደራጀት አገራችንን ውስጥ ለውስጥ ሲቦረቡሩና ሀብቷን ሲዘርፉ ነበር። አብዮቱ ከፈነዳም በኋላ ነፃ እንወጣለን በማለት ትግል የጀመሩ እንደወያኔ የመሳሰሉ ቡድኖችን በማስታጠቅና በማደራጀት አገራችን ዛሬ ላለችበት አስከፊ ሁኔታ ከፍተኛ አስተዋፅዖ አድርጓል። አገሪቱ በሁሉም አቅጣጭ በጦርነት እንድትወጠርና ማዕከላዊው መንግስት እንዲዳከም ያላደረገው ጥረት ይህ ነው አይባልም። ከዚህ ስንነሳ በአንዳንድ ኢትዮጵያውያን ነን በሚሉና ዛሬ በአሜሪካን ምድር ተደላድለው በሚኖሩ አንዳንድ የድሮ ባለስልጣኖች የሚነገረው አባባል፣  የእነ ኢሳያስ ቡድን „ኢትዮጵያ እንድትገነጣጠል አይፈልግም“ የሚለው አባባል ከተጨባጩ የኢትዮጵያ ሁኔታና ከኮመን ሴንስም ሆነ ከሎጂካዊ አቀራረብ ጋር በፍጹም የሚጣጣም አይደለም። ይህ ብቻ ሳይሆን፣ እነዚህ „የኢትዮጵያ ተቆርቋሪዎች“ በእዚህ ዐይነት አቀራረባቸው የሚያረጋግጥሉን ስለዲሞክራሲና ስለ ነፃነት ያላቸውን እጅግ የተዛባ አመለካከት ነው። ለመሆኑ የእነ አቶ ኢሳያስ ቡድን ኢትዮጵያ እንዳትበታተን የሚፈልግ ከሆነ ለምን ወያኔንና የኦሮሞ ነፃ አውጭ ድርጅቶችን አስታጠቀ ?  እነዚህ ትላልቅ ስዎች ያልገባቸው ነገር የእነ ኢሳያስ ዋናው ዓላማ ኢትዮጵያን ከውስጥ መቦርቦርና ማዳከም ብቻ ሳይሆን፣ የወታደሩ አገዛዝ አትክሮው ሁሉ ወደ ጦር ሲያመራና ኃይሉንና ሀብቱን በጦርነት ላይ ሲያውል መዳከም ይጀምራል፤ እኛም በቀላሉ ልናሸንፈው እንችላለን ከሚለው ስሌት በመነሳት ደርግን የሚቃወሙ ኃይሎችን ሁሉ ማስታጠቅና ማደራጀት እንደነበር በፍጹም የተረዱ አይመስልም። ስለሆነም የእነ ኢሳያስ ድርጊት በቀጥታ ኢትዮጵያ እንድትበታተን ከመደገፍ ውጭ ሊታሰብ አይችልም።   እነ አቶ ኢሳያስ በሁሉም አቅጣጫ ጦርነት እንዲከፈት ሁኔታውን ሲያመቻቹና እንገነጠላለን ያሉ ኃይሎችን ሁሉ ሲደግፉ ማዕከላዊው አገዛዝ የግዴታ ለኢኮኖሚ ግንባታና ለሌሎች ስራዎች ሊጠቅምበት ወይም ሊያውል የሚችለውን ሀብት ጦርነት ላይ እንዲያውል ተገደደ።  ከውስጥ የሰው ኃይልም ሆነ ሀብት እንዲወድም ተደረገ። በሌላ ወገን ግን በዚህ ዐይነቱ እርኩስ ተግባርና ተንኮል የኤርትራ ተገንጣይ ቡድኖችና ሰፊው የኤርትራ ህዝብም በምንም ዐይነት ተጠቃሚ ሊሆኑ አልቻሉም። በከፍተኛ ምሁራዊና በሳይንሳዊ አስተሳሰብ ላይ ተደግፎ የተካሄደ እንቅስቃሴና ጦርነት ባለመሆኑ የመጨረሻ መጨረሻ የጨለማ ኑሮ ውስጥ ሊወድቁ ቻሉ።  እንደገና ሊያገግሙ የማይችሉበት ሁነታ ውስጥ ወደቁ። አገዛዙ ብቻ ሳይሆን ሰፊው የኤርትራ ህዝብና በተለይም ወጣቱ በቀላሉ መፍትሄ የማይገኝለት የሳይኮሎጂካል ቀውስ ውስጥ ነው የወደቁት። በቀላሉ ራሳቸውን በራሳቸውን ማግኘት እንዳይችሉና እየባነኑ እንዲኖሩ ነው የተደረጉት። ከዚህ ስንነሳ ኤርትራ ያለቀላት አገር ነች። በምንም ዐይነት እንድገና በራሷ ጥረት አገግማ ካለበት ሁለመንታዊ በሽታ ድና ልትነሳ አትችልም። ህዝቡ፣ በተለይም ወጣቱ ከፍተኛ የሆነ የህሊና ጥገና ድጋፍ የሚያስፈክልገው ነው። ራሱን በራሱ ለማወቅ የብዙ መቶ ዐመታት ጉዞና ህክምና ያስፈልገዋል። አገዛዙም በዲሞክራሲያዊ ብቻ ሳይሆን በከፍተኛ ደረጃ በሚያስብ ኃይል እስካልተለወጠ ድረስ ለአገራችንና ለአካባቢው አገሮች የሰላም ጠንቅ ነው የሚሆነው። በሌላ ወገን ደግሞ በኢርትራ ውስጥ ዲሞክራሲያዊና ሰብአዊ  ስርዓት ለማምጣት በፍጹም አይቻልም። የተገለጸለት ኃይል ባለመኖሩ የኤርትራ ህዝብ እጣ የጨለማና የመሰደደ ኑሮ ብቻ ነው የሚሆነው።

ይህ ሁኔታ ምንን ነው የሚያረጋግጥልን ? ዛሬም ሆነ ወደፊት፣ በዚህ አገዛዝም ሆነ በሌላ አገዛዝ ኤርትራ ውስጥ ያለው አገዛዝና ወደፊትም ቢሆን ኢሳያስን የሚተካው ግለሰብም ሆን ቡድን ከደሙ ጋር የተዋሃደ ጭንቅላቱን አንቆ የያዘው የጨለመ አስተሳሰብ ስላለ ከበጥባጭነትና ከጦርነት ቀስቃሽነት በፍጹም ሊላለቀቅ አይችልም። ወጣቱና ሰፊው ህዝብም የዚህ የጨለማ አስተሳሰብ ሰለባ ስለሆነና በቀላሉ ሶሻላይዝድ ሊሆን ስለማይችል በኢትዮጵያና በኤርትራ መሀከል ሊፈጠር የሚችለው ግኑኝነት ምናልባት  ከመቶና ከሁለት መቶ ዐመታት በኋላ የሚሆን ይሆናል። ዛሬ በአንዳንድ የዋህ ኢትዮጵያውያን የእነ ኢሳያስን አገዛዝ ለኢትዮጵያ አሳቢ አድርጎ ለማቅረብ መሞከርና፣ ውስጥ ያለንን ችግር ለመፍታት የሚያስችል አቅም ሳይኖረን በኤርትራና በኢትዮጵያ መሀከል ስለሚኖረው የወደፊቱ ግኑኝነት ደፋ ቀና ማለትና ሰሚናሮች ሲዘጋጁ ስናይ ይህ ደፋ ቀና የሚለው ኢትዮጵያዊ ኃይል ሁኔታው የቱን ያህል ያለተገለጸለት መሆኑን ነው የምንገነዘበው። አንዳንድ ድርጅቶችና ግለሰቦች የሚሰሩት የማያስፈልግ ስራና ቅስቀሳ ብዙውን የዋህ ኢትዮጵያዊ እያሳሳተው ነው። በሌላው ወገን ግን በኤርትራና በኢትዮጵያ መሀከል ወደፊት ጥሩ ግኑኝነት እንዲመሰረት ከተፈለገ ቀናና ተራማጅ አስተሳሰብ ያላቸውን ኤርትራውያንንን መደገፍና ከእነሱ ጋር አብሮ መስራት አስፈላጊ ይመስለኛል። በግልጽ ለመወያየት ከፈለጉ ድረስ በሩን ክፍት ማድረግ ያስፈልጋል። በአካባቢው ዘላቂ ሰላም እንዲመጣ ከተፈለገ ተራማጅና በሰብአዊነት መርሆች ላይ የተመሰረተ ሰፋ ያለ ምሁራዊ እንቅስቃሴ ያስፈልጋል። ስለሆነም የኢትዮጵያ ተራማጆችና የስብአዊነት አስተሳሰብ አራማጆች ከኤርትራውያን ተራማጆችና የሰብአዊነት  ጠበቃዎች ጋር ቢሰሩና ሃሳብ ለሃሳብ ቢለዋወጡ ሁለቱም ህዝቦች ዕውነተኛ ወዳጅነትን ሊፈጥሩና፣ ቀጥሎም ወደ ኮንፌዴሬሽንና ከዚያ በኋላ ዳግሞ ሁኔታው ሲበስል ወደ ውህደት ሊያመሩ የሚችሉበት ሁኔታ ሊፈጠር ይችላል። ይህ ጉዳይ ሊታሰብ የሚችለው ከእነ ኢሳያስ ስሌትና አገዛዝ  ባሻገር ነው።

ያም ተባለ ይህ፣ በአጠቃላይ ሲታይ በኢትዮጵያ ውስጥ የብሔረሰብ እንቅስቃሴ መዳበርና ነፃ እንውጣ እያሉ እዚህና እዚያ የጦር ትግል ማካሄድ ከአጠቃላዩ የተበላሸ ፊዩዳላዊ አመለካከትና የሪፑብሊክ መንፈስ እጦትና ከተበላሸ የኢኮኖሚና የማህበራዊ ፖሊሲ ጋር የተያያዘ ነው። ያልተስተካከለ ዕድገት ወይም የተዛባ የኢኮኖሚ ፖሊስ የግዴታ ተጨቆን ለሚሉ ኃይሎች መፈናፈኛ መንገድ በመስጠት ያለውን ክፍተት ተጠቅመው በመሰረቱ በአገሪቱ ላይ ዘመቻ እንዲያካሂዱ ረድቶአቸዋል። ስለሆነም የብሄረሰብ እንቅስቃሴ በጊዜው የነበረው እጅግ የተዳከመ ኢኮኖሚና የህብረተሰብአዊ አወቃቀር ውጤትና በአገሪቱ ምድር ዲሞክራሲያዊ መብቶችና በነፃ መደራጀት ካለመቻል ጋር የተያያዙ ናቸው ማለት ይቻላል። የዚህኛው ወይም የዚያኛው ብሄረሰብ ተወካይ ነኝ የሚለው ኤሊት የስልጣን ተካፋይ አይደለሁም ብሎ  የሚያራግበው ወሬ እንጂ በመሰረቱ ጥያቄውም ሆነ እንቅስቃሴዎቹ በምንም ዐይነት ሰፊውን የኦሮሞ ብሄረሰብም ሆነ የኤርትራ ህዝብ የሚመለከቱና የሚወክሉ አልነበረም።  የእንቅስቃሴያቸው አጀማመርና ጎልቶ መታየት ተራማጅ የሚያስመስላቸው ቢመስልም፣ ከዛሬው ሁኔታ ተነሰተን  እንቅስቃሴያቸውን ስንመረምር በብሄረሰብ አካባቢ ብቻ መሰባሰቡና ትግል መቀጠሉ ዕውነተኛ የነፃነት ትግል እንዳያራምዱ አድርጎአቸዋል። እንቅስቃሴያቸው  እየጎለመሰ ሲመጣ ሳይንሳዊ መልክ እያጣና ነፃነት ተቀናቃኛች በመሆን የባሰውኑ የጥቁርን ህዝብ ነፃነትና ዕድገት በሚጠሉ የውጭ ኃሎች ጉያ ስር እንዲወድቁ አስገድዷቸዋል። እራሳቸው ነፃ እንወጣለን ብለው መንቀሳቀስ የጀመሩት ድርጅቶች ከዚህም ከዚያም ዕርዳታ በማግኝት በታሪካቸው ላይ ብቻ ሳይሆን የዘመቱት፣ ያለሙትንም ነፃነት መጎናጸፍ እንዳይችሉ ተደርገዋል። በዚህም መልክ እንቅስቃሴያቸውን ከብሔራዊ ባህርይው በማውጣትና ዓለም አቀፋዊ መልክ እንዲኖረው በማድረግ  ኢትዮጵያንና ዕድገቷን ለሚጠሉ አገሮችና በሃይማኖት ስም ተጥቀመው አገራችንን ለመበታተን ለሚፈልጉ ኃይሎች ሁኔታው እንዲመቻች ለማድረግ በቅተዋል። ስለሆነም የጦር ትግላቸው በአገዛዙ ላይ ብቻ ያተኮረ ሳይሆን የገዢው መደብ ተጠቃሚ ነው በሚለው የህብረተሰብ ክፍል ላይ፣ በተለይም በአማራው ላይ ጦርነት በመክፈት የብዙ ሰዎች ህይወት ተቀጠፈ፤ ብዙ ንብረትም አወደሙ። በሌላ ወገን ግን ይህ ዐይነቱ በየብሄረሰብ አካባቢ የተደረገ እንቅስቃሴ የኢትዮጵያዊነት ስሜት እንዲደመሰስ አደረገ። በተለይም ወጣቱ እየተመለመለ በመግባትና በጥላቻ ስሜት እንዲመረዝ በመደረጉ ብሄራዊ ወይም አገራዊ ስሜቱ ሙሽሽ ብሎ እንዲወድም ተደረገ። ይህ ዐይነቱ በኢትዮጵያ ላይ መዝመትና የኢትዮጵያዊነት ስሜት ደብዛው እየጠፋ መምጣት በአንድ ወቅት ብሄራዊ አጀንዳ ይዘው ይታገሉ የነበሩ ግለሰቦችንም የብሄረሰብ አርማ ይዘው እንዲያራግቡ አስገደዳቸው። በተለይም የወያኔ አገዛዝ ስልጣን ከያዘና ከኦሮሞ ህዝብ የነፃነት ድርጅት(OLF) ጋር አገር በሚያስተዳድሩበት ጊዜ፣ አንድ ወቅት ማርክሲስት ወይም ሶሻሊስት ነኝ እያለ ያዙኝ ልቀቁኝ ይል የነበረው ሁሉ የቤተሰቡን ግንድ በመቁጠር እኔም ኦሮሞ ነኝ ማለት ጀመረ። ይህ የሚያሳየው የቱን ያህል የመንፈስ መረጋጋት አለመኖርና አርቆ አለማሰብን ነው፤ ለስልጣን መስገብገብንና በፕሪንሲፕል አለመመራትን ነው። እነዚህ ኃይሎች ወይም ግለሰቦች ዛሬ ደግሞ 180 ዲግሪ በመዞር እንደገና የኢትዮጵያ ጠበቃ በመሆን ወጣቱ ከድሮ አባቶቻችን መማር ያለበት ነገር አለ በማለት ሲናገሩ ይሰማል።

     የወያኔ የክልል ፖሊሲና ጠንቁ !

በመጀመሪያ ደረጃ በተለይም አብዮቱ ከፈነዳም ሆነ ከመፈንዳቱ በፊት ብቅ ያሉትንና ወደ ጦር ትግል ያመሩትን የብሄረሰብ እንቅስቃሴዎች የፖለቲካ ንቃተ-ህሊና ሁኔታ ስንመለከት፣ አብዛኛዎቹ በጊዜው የግራ ስም ቢይዙም ወይም በማርክሲዝም ሌኒንዝም ስም ቢምሉም ርዕያቸውም ሆነ ትግላቸው በምንም ዐይነት ከሶሻሊዝም ጋር ወይንም ከማርክሲዝም ጋር የተያያዘ አልነበረም። ትግላቸውን ለመጀመር ሲነሳሱ፣ በጊዜው የነበረው ጭቆና በብሄር ላይ የተመሰረተ ሳይሆን ፊዩዳላዊ ባህርይ ያለውና፣ ይህ ጭቆና ጠቅላላውን የአገሪቱን ህዝብ የሚመለከት እንደነበር በፍጹም አልተገነዘቡም። የተወሰነው የገዢ መደበ ከአማራው ብሄረሰብ በመውጣቱ የአማራውን ብሄረሰብ ብቻ የሚጠቅም፣ የኑሮውን ደረጃ የሚያሳድግለትና ከሌሎች ብሄረሰቦች የበለጠና የተለየ መሆኑን የሚያሳይ ልዩ ዐይነት ፖለቲካና የኢኮኖሚ ፖሊሲ የተከተለ አድርገው ነበር የቆጠሩት።

የሞናርኪውን አገዛዝ ጠቅላላውን የፖለቲካ አወቃቀርና ፍልስፍናውን ስንመለከት ግን፣ አገዛዙ የፊዩዳሉን፣ የአሪስቶክራሲውንና የንጉሳውያን ቤተሰብን ጥቅም የሚያስጠብቅ ነበር። ርዕዮተ-ዓለሙንም ስንመለከት ፊዩዳላዊና የንጉሱን ፍጹማዊነትና አገራችንን ለመግዛት ከእግዚአብሔርር የተላኩ ናቸው በማለት ሰፊው ህዝብ አምኖ እንዲቀበል የሚያደርግ እንጂ በመሰረቱ አማራ ብሔረሰብ የሚባለውን ርዕይ የሚያንፀባርቅ አልነበረም። በተለያዩ የህብረተሰብ ታሪኮችም ውስጥ እንደታየው ስልጣን ላይ ያሉ የገዢ መደቦች የሚከተሉት ፖሊሲና ርዕዮተ-ዓለም ሁልጊዜ ከራሳቸው ጥቅምና ከሚደግፋቸው የህብረተሰብ ክፍል በመነሳት እንጂ የአንድን ህዝብ ወይም ብሔረሰብ ጥቅም አጉልቶ በማሳየት አይደለም።  ከዚህ ስንነሳ የኦርቶዶክስ ሃይማኖትና በዘፈንም ሆነ በምግብና በአለባበስ የሚገለጸው የአማራ ባህል ነው የሚባለው በመሰረቱ የአማራዉ ብቻ አልነበረም። አይደለምም። እነዚህ ዐይነት በልዩ ልዩ መልክ የሚገለጹ ባህሎች ከህብረተሰቡ ዕድገት ጋር  በህበረተሰብአዊ ሂደት ታሪክ ውስጥ ሰዎች አውቀውም ሆነ ሳያውቁ ያዳበሩት ነው። በተጨማሪም በአንድ አካባቢ የሚዳብር ባህል ከተለያዩ አካባቢዎች ከመጡ የህብረተሰብ ክፍሎች ጋር በመዋሃድ ልዩ ዐይነት ዕምርታን የሚያገኝ ነው። በመሰረቱ በአንድ አካባቢም ሆነ ህብረተሰብ ውስጥ የሚፈልቅና የሚዳብር ባህል የተለያዩ ባህሎች ጥምር ውጤት(Synthetic) ነው። ስለሆነም ይህ የአማራው ባህል ነው፣ ያኛው የኦሮሞ ነው ብሎ መጥራት በጣም ያስቸግራል።   አንድን ባህል ወይም ባህሎች ከላይ ወደ ታች የምትጭናቸው ነገሮች አይደሉም። የሰው ጭንቅላት ውጤቶች በመሆናቸው እንደየህብረተሰቡ የዕድገት ደረጃ እየተሻሻሉና ልዩ መልክ እየያዙ የሚሄዱ ናቸው፤ ወይም ቀጭጨው በመቅረት ለዕድገት፣ ለሰፊና ለተገለፀለት አስተሳሰብ እንቅፋት ይሆናሉ።

በዓለም አቀፍ ደረጃ ርዕዮተ-ዓለም የአገዛዝ መሳሪያ ሆኖ ከመታወቁ በፊት በአጋጣሚና ሰዎች በአንድ አካባቢ ሲሰባሰቡና ልዩ ህብረተሰብአዊ ግኑኝነት ሲፈጠሩ የሚያዳብሩት ነው። በሌላው ወገን የሃይማኖትን ጥያቄ ስንመለከት ከደብቡ ይልቅ በመጀመሪያ ደረጃ በኃይል ተግባር የሆነው በአክሱም ግዛትና አካባቢው ብቻ ነው። የኋላ ኋላ ተቀባይነትን በማግኘት የተስፋፋ ነው ማለት ይቻላል። የአማርኛን ቋንቋና የግዕዝን ፊደል አመሰራረት ስንመለከት የህዝብ ቋንቋ የነበሩና በገዢውም መደቦች ቅርጽ በማግኝት የተስፋፉ ናቸው። ስለሆነም የአማርኛ ቋንቋ ልዩ የሆነና የጠቅላላው ህዝብ መግለጫ እየሆነ የመጣ ነው። እንደሚባለው ከሆነ ወደ 50% የሚሆኑ ቃላቶች ከኦሮምኛ ተወሰደዋል። በመሰረቱም ቋንቋ ሊዳብር የሚችለው ከሌሎች ቋንቋዎች ጋር ሲገናኝና ሲዋሃድ ብቻ ነው። ለምሳሌ በጀርመንኛ ቋንቋ ውስጥ የእንግሊዘኛም ሆነ የፈረንሳይኛ ቃላቶች ተካትተዋል። በመሆኑም የአማርኛን ቋንቋ እንደ አገዛዝ መሳሪያና የአንድ ብሄረሰብ ቋንቋ አድርጎ መውሰዱ ስሀተት ብቻ ሳይሆን እጅግ አደገኛም ነው። ጠቅላላው ህዝብ ደንቁሮ እንዲቀር የሚደረግ በማወቅም ሆነ ባለማወቅ ዘመቻ የሚካሄድበትና፣ በተለይም የውጭ ኃይሎች እንግሊዝና አንዳንድ የምዕራብ አውሮፓ አገሮች ከ1920ዎቹ ዓመታት ጀመሮ የሚያካሂዱት የማዳከምና፣ ህዝባችንን በጦርነት ዓለም ውስጥ በመንከር ርስ በርሱ እንዲጨፋጨፋ ለማድረግ የታቀደ የኢምፔሪያሊስቶች ሴራ ነው። በዚህ ዐይነቱ ሴራ ውስጥ ነው ወያኔም ሆነ በዚህም ሆነ በዚያኛው የስለላ ድርጀቶች የሰለጠኑ ኢትዮጵያውያን ዘመቻ የሚያካሂዱትና ለመጨራሻ ጊዜ የኢትዮጵያን ውድቀት የሚያፋጥኑት።

ያም ሆነ ይህ በአገራችን ምድር በብሄረሰብ ስም የተካሄደውና የሚካሄደው እንቅስቃሴና ጦርነት ፍልስፋና አልባና የዕውነተኛ ነፃነት መሰረት የሌለው ነው። በመጀመሪያ ደረጃ በማርክስዝምና በሶሻሊዝም ስም የሚምልና መመሪያው ያደረገ ትግልንና እንቅስቃሴውን በብሄረሰብ ደረጃ ሊገድበው አይገባም። ይህ ዐይነቱ አካሄድ ዓለም አቀፋዊ ባህርይ ያለውንና „ሁሉም ጭቁን ህዝቦች በአንድነት ተባብራቸሁ ተነሱ“  የሚለውን መፈክርና መመሪያ የሚቃውም ነው። እነ ሮዛ ሉክሰምበርግ የብሄረሰቦችን „የራስን ዕድል በራስ መወሰ“ን የሚለውን መፈክር ሲቃወሙ በመሰረቱ እንደዚህ ዐይነቱ አካሄድ ዓለም አቀፋዊነትንና ዕውነተኛ ነፃነትን የሚቃወምና፣ የነፃነትንንም ትግል የሚያደናቅፍ መሆኑን በመገንዘባቸው ነው። ከፕላቶን ፍልስፍና አንፃር ስንነሳ ደግሞ የሰውን ልጅ የማሰብ ኃይልና በዕውቀት አማካይነት በማዳበር ለሁሉም ዜጋ የሚስማማ ህብረተሰብን ለመመስረት የሚያስችለውን አካሄድ የሚያደናቅፍ ነው። የሰውን የማሰብ ሃይል የሚገታና ተጨናግፎ እንዲቀር የሚያደርግ ነው። አንድ ግለሰብም ሆነ ብሄረሰቦች እግዚአብሔር የሰጣቸውን በልዩ ልዩ መልክ የሚገለጸውን የማሰብ ኃይላቸውንና የፈጠራ ችሎታቸውን እንዳያዳብሩ የሚያግድ ነው። በዚህም ተባለ በዚያ የብሄረሰብ ጥያቄ በአንድ አገር ውስጥ ከሰፈነ አጠቃላይ የጭቆናና የፀረ-ዕድገት ፖሊሲ ጋር የተያያዘ ሲሆን ሊፈታም የሚችለው ጥቂት የብሄረሰብ ተወካይ ነን በሚሉትና በሚያካሄዱት የጦር እንቅስቃሴ አማካይነት አይደለም። ዕውነተኛ የነፃነትና የዕድገት እጦት በዚህ ዐይነቱ የፍልስፍና አልባ አካሄድ ተግባራዊ እንደማይሆን ከኤርትራው ትግልና  ውጤቱ መማር ይቻላል። እንደምናየው ውጤቱ ፋሽሽታዊ አገዛዝና የጨለማ ኑሮ ነው። ውጤቱ ድህነትና መሰደድ ነው። ውጤቱ የህሊና ድቀትና ጠባብ አስተሳሰብን መጎናፀፍ ነው። በአጭሩ ውጤቱ ነፃነት ሳይሆን፣ በልዩ ልዩ መልክ የሚገለጽ የነፃነት እጦት ነው። አንድ ዲስፖቲያዊ አገዛዝ በመመስረትና ጦርነትን ፍልስፍናው በማድረግ አንድ ህዝብ ዘለዓለሙኑ እየተሰቃየ እንዲኖር የሚያደርግ ነው።

ከዚህ ሁኔታ ስንነሳ የወያኔ የክልል ፖሊሲ እንደምናየው ለየብሄረሰቦች ዕውነተኛ ነፃነትን ያጎናፀፈ አይደለም። ለከፋፍለህ ግዛ የሚያመች ፖሊሲ በመሆኑ፣ በየክልሉ አዲስ የዋር ሎርዶች(War Lords) እንዲፈልቁና ህዝቡን አድኸይተውና አደንቁረው ራሳቸው ተመቻቸውና ደልቶአቸው እንዲኖሩ አዲስ ሁኔታ ተፈጥሮላቸዋል። በየአካባቢው ያለውን ሁኔታ ስንመለክት በዕቅድ የሚስራ ስራ የለም። ከተማዎችና መንደሮች በዕቅድ የተገነቡ ሳይሆኑ የድሮውን ሁኔታ በማባባስ ህዝባችን ከእንስሳ በታች እንዲኖር የተደረገበትን ሁኔታ እንመለከታለን። በየአካባቢው በልማት ስም የሚካሄዱት እንቅስቃሴዎች የአበባ ተከላዎችና የስኳር አገዳ ተከላዎች ናቸው። ጨአትና ቡና በመትከል ህዝቡን ማደንዘዝና የውጭ ከረንሲ ለመቃረም የሚደረግ ሩጫ ነው። ያለፉትን የ25 ዓመታት የክልል ፖሊሲ ስንመለክት በህዝባችንና በታሪካችን ላይ ውድቀትን ያስከተለ ነው። እያንዳንዱ ግለሰብ እንደሰው የማሰብ ኃይሉን እየተጠቀመ እንዳይኖር የተደረገበት ሁኔታ በአገሪቱ ውስጥ ሰፍኗል። ይህ ዐይነቱ በብሔረሰብ ነፃነትና የራስን ዕድል በራስ መወሰን በሚለው ስም የሚካሄድ ፖለቲካ ለህብረተሰብአዊና ለሀብት እንቅስቃሴ(Social and Capital mobility) እንቅፋት የሆነ ነው። በአገሪቱ ውስጥ አጠቃላይ ህብረተሰብአዊ ሀብት(Soical Wealth)እንዳይዳብር ያገደ ነው። ይህ ዐይነቱ አካሄድ በተለይም የአረብ አገሮችና ዕድገታችንን የሚቃወሙትንና፣ በተለያዩ ድሮች ያሰሩንን ኢምፔሪያሊስት ኃይሎችን ጥቅም የሚያስጠብቅ ነው። ሳይንስና ቴክኖሎጂ እንዲሁም የባህል ዕድገትና ምጥቀት እንዳይኖር የሚያግድና ድህነትን ያስፋፋና የሚያስፋፋ ነው። በመሰረቱ እንደዚህ ዐይነቱ ፖሊሲ የተፈጥሮንና የህብረተሰብ ህግን የሚፃረር እጅግ አደገኛ አካሄድ ነው። የሰውን ልጅ ወይም የእያንዳንዱን ዜጋ  የማደግ ፍላጎት የሚያግድ ነው። በአንድ አገር ውስጥ ያለን ሀብት በስነ-ስርዓት እያወጡ በኃይልና(Energy) በማሽን አማካይነት እየተደገፉ በማምረት የሰውን ፍላጎት ለሟሟላት እንዳይቻል እንቅፋት የሚሆን ነው። በተፈጥሮና በሰው ልጅ መሀከል የሚኖረውን መደጋገፍና፣ እንዲሁም ደግሞ በሰዎች መሀከል በልዩ ልዩ መልከ መዳበር ያለበትንና ሊገለጽ የሚችለውን ግኑኝነት የሚጻረር ነው። የሰውን ልጅ ተፈጥሮአዊ የማሰብ ኃይል የሚያፍን  የነፃነትና የዕድገት እንቅፋት ነው።

በመሰረቱ ከትግሬ ብሔረሰብ ወጣሁ የሚለውና ሃያአምስት ዐመታት ያህል አገራችንን የሚቆጣጠረውና የሚያተራምሰው አገርን የሚያዳከም እንጂ የብሔረሰቦችን መብት ተግባራዊ የሚያደርግና ነፃነታቸውን እንዲቀዳጁ የሚያደርግ አይደለም። እንደዚሁም የራሱን የትግሬን ብሄረሰብ ወይም ሰፊውን ትግሬን የሚጠቅም አይደለም። በዚያው ደንቁረው የሚያሰቃራቸው ነው። በሌላ ወገን ደግሞ ለብሄረሰቤ ነፃነት የተጋልኩ ነኝ፣ ለዚህም ጠበቃ የቆምኩ ነኝ ካለና ድልን ከተቀዳጀ በኋላ መቀሌ ጠቅልሎ መግባት ነበረበት። መሀከል ከተማ ውስጥ ሆኖ በብሄረሰብ ስም ነፃነትና የራስን ዕድል በራስ መወሰን ስም እየተመጻደቀ በታሪክና በህዝብ ላይ መቀለድ አልነበረበትም፤ የለበትም። ታስቦም ሆነ ሳይታሰብ ወያኔ እዚህ ደረጃ መድረሱና በአገሪቱ ውስጥ ለሚገኙ ልዩ ልዩ ብሄረሰቦች አርቲፊሻል መለያ መስጠቱ ለጊዜው የጠቀመው ቢመስልም፣ አንድ ቀን ህዝቡ ሆ ብሎ በአንድ ላይ ሲነሳ በወያኔ ላይ ብቻ ሳይሆን በጠቅላላው በትግሬ ብሄረሰብና በዚህም በዚያም ብሎ ጥቅም አግኝቻለሁ ብሎ በሚሯሯጠው ላይ እንደሚነሳና መግቢያ እንደሚያሳጣው የታወቀ ነው። ስለሆነም የመጨረሻ መጨረሻ የትግሬ ብሄረሰብ እንዳለ ነው የሚጎዳው ማለት ይቻላል። በመሰረቱ ግን ወያኔ የተከተለው ፖለቲካ የትግሬን ብሄረሰብ እንዳለ የሚጠቅም ሳይሆን በቤተሰብ የተሳሰረ በአዲስ የገዢ መደብ የሚደገፍና፣ ከኤርትራ በመጡ በማፊያ መልክ በተደራጁ ኃይሎች የተከበበና በኢምፔሪያሊስት ኃይሎች የሚጠመዘዝና ማንኛውንም ድጋፍ የሚያገኝ ነው። ስለሆነም ህብረተሰብአዊ ትርምስና ድህነት እዚያው በዚያው እንዲቀጥሉ በማድረግ ህዝባችን የዕውነተኛ ስልጣኔ ባለቤት እንዳይሆን የሚያደርግ እጅግ አደገኛ አካሄድ ነው። ዛሬ በአዲስ አበባ ውስጥ በየቦታው የሚታየው እጅግ አፀያፊ ተግባርና ሰፊው የአዲስ አበባ ህዝብ በቆሻሻ ቦታዎች እንዲኖር መገደዱ ከስግብግብነትና ከማን አለብኝነት ጋር የተያያዘ ነው። ጥቂት ግለሰቦችና ቡድኖች ከውጭ ኃይሎች ጋር በጥቅም በመተሳሰርና ተላላኪ በመሆን የታሪክን ሂደት በማጣመም በቀላሉ ልንወጣው የማንችለው የተወሳሰበ ችግር ውስጥ ጥለውናል ማለት ይቻላል።

ይህ ዐይነቱ አካሄድ በአንድ አገር ውስጥ የሚኖርና ከዚህም ሆነ ከዚያኛው ብሄረሰብ የተውጣጣ ግለሰብ እንደሰውና እንደዜጋ እንዳይታይ የሚያደርግ ብቻ ሳይሆን የአገሩን ስም በስሙ እንዳይጠራ የሚያስገድደው ነው። በአንድ አገር ውስጥ ተወልዶ የአገሩን ስም እንዲጠራ ሳይሆን፣ ከአንድ ክልል ተወለድኩ ብሎ እንዲጠራ የሚያስገድደው ነው። „ከእናቴ ሳይሆን ከማህፀኗ ነው የተወለድኩት“ ብሎ እንደመናገር ዐይነት አስተሳሰብ ተስፋፍቷል፤ የጊዜው ፈሊጥም ሆኗል። ይህ ዐይነቱ ዘመቻና ጥላቻ በመሰረቱ አንድነትንና ሁለንታዊነትን፣ ወይም ደግሞ በአንድ ነገር የተጠቃለለን ግን ደግሞ ልዩ ልዩ ነገሮችን የያዘውን የተፈጠሮን ህግ የሚቃወም ነው። ተፈጥሮም ሆነ ሰው በአንድነትና በልዩ ልዩ ነገሮች ብቻ ነው የሚገለጹት። በአንድ በኩል እንደ ግለሰብአዊ፣ በሌላ ወገን ደግሞ እንደ ህብረተሰብአዊ አካል። ሰውነታችንም እንደዚህ አንድም ሁለንታዊም ነው። ማንኛውም ሰው እንደሰው የሚገለጸውና እንደሰውም የሚኖረውና የሚያስበው የተለያዩ ኦርጋኖችና የተለያዩ የሰውነት ክፍሎች ሲኖሩት ብቻ ነው። እንደሚታወቀው የተለያዩ የሰውነት ክፍሎች በስራ-ክፍፍል የተደራጁና፣ በሌላ ወገን ደግሞ ስራቸውን በማቀነባበር እንደሰው እንድንቀሳቀስ፣ እንድናሰብና እንዲሁም እንድንፈጥርና እንድንሰራ የሚያደርጉን ናቸው። ከዚህ ስንነሳ በብሄረሰብ ስም ተሳቦ በወያኔ ተግባራዊ የሆነው የክልል ፖለቲካ  ይህንን ተፈጥሮአዊ ህግ ወይም ዩኒቨርሳል ህግ የሚቃወም ነው። የኢትዮጵያ ህዝብ ጠላት ብቻ ሳይሆን የጠቅላላው ህዝብም  ጠላት ነው ማለት ይቻላል።

የኢትዮጵያ ጠንቆችና ኢትዮጵያዊነትን የሚቀናቀኑ አካሄዶች !

ኢትዮጵያዊነትን አጉልቶ የሚጠራ ወይም ሞትኩልሽ እያለ ባንዲራ የሚያውለበልብና፣ ለስልጣን ብሎ እዚህና እዚያ የሚሯሯጥ ሁሉ ዕውነተኛ ኢትዮጵያዊ ወይም ሰው ነው ሊያሰኘው የሚያስችል አይደለም። ላይ ለማሳየት እንደሞከርኩት አፄ ኃይለስላሴና ደርግም ኢትዮጵያውያን ቢሆኑም በመሰረቱ የኢትዮጵያን አንድነትና የህዝቦቿን ፍላጎት አናግተው ነው የሄዱት። በመሰረቱ አንድ የገዢ መደብ ስልጣን ላይ በሚቆይበት ጊዜ የገዢ መደብ ነኝ ብሎ ለመመፃደቅ ሳይሆን መስራት ያለባቸው ታሪካዊና ህብረተሰብአዊ ግዴታዎች አሉ። አንድ መንግስትና በአንድ አገር ውስጥ ያለ ሀብት  የገዢ መደቦች የግል ሀብት አይደሉም። በአንድ አገር ውስጥ ያለ ሀብት የጠቅላላው ህዝብ ሀብት ነው። መንግስትም ሆነ የመንግስት መኪና የህዝብ ተወካዮች እንደመሆናቸው መጠን አባትና እናት ልጆቻቸውን መንከባከብና በስነስርዓት ማሳደግ እንዳለባቸው ሁሉ አንድ የገዢ መደብና መንግስታዊ መዋቀሮች የአንድን ህዝብ መሰረታዊ ፍላጎት በማሟላት ወደ ሚቀጥለው የዕድገት ደረጃ ለመሸጋገር አስፈላጊዊን ቅድመ-ሁኔታዎች ማዘጋጀት አለባቸው። ለዕድገት የሚሆኑ አመቺ ሁኔታዎችን መፍጠር አለባቸው። ከዚህ ስንነሳ በተለይም የአፄው አገዛዝ የኢትዮጵያን ህዝብ ጥቅም ያሰጠበቀና አገሪቱ በፀና መሰረት ላይ እንድተገነባ ማድረግ የቻለ አልነበረም።

በመሆኑም በአንድ በኩል ኢትዮጵያ አገሬ እያሉና ባንዲራ እያውለበለቡ፣ በሌላ ወገን ደግሞ  የኢትዮጵያን ህዝብ ደህንነትና ብልጽግና እንዲሁም አገራችን የሳይንስና የቴክኖሎጂ ባለቤት እንዳትሆን አጥብቀው የሚታገሉና ከተለያዩ የኢምፔሪያሊስት ኃይሎች ጋር የሚሰሩ ትላልቅ ሰዎች የሚመስሉ አሉ። በአብዛኛዎቻችን ዘንድ የተደረሰበት መደምደሚያ እዚህና እዚያ የሚንቀሳቀሱ የብሔረሰብ እንቅስቃሴዎች ብቻ ለአገሪቱ ደህንነት አደገኛ እንደሆኑ ነው። ከነዚህ ይልቅ እስከዛሬ ውስጥ ለውስጥ እንደነቀርሳ የሚሰረስረን በመሰረቱ ከፊዩዳላዊ አስተሳሰብ ያልተላቀቀና፣ ጥቅሙንና ህልሙን በተለይም ከአሜሪካን ኢምፔሪያሊዝም ጋር ያገናኘ የድሮው ቢሮክራሲና የአሪስቶክራሲ ልጅ፣ እንዲሁም ደግሞ አዲስ ብቅ ብቅ ያሉ የዓለምን ፖለቲካና ኢኮኖሚያዊ አወቃቀር በደንብ ያላገናዘቡ ኤሊት ነን ባዮች ናቸው ለአገራችን አንድነትና መበልጸግ ጠንቆች የሆኑትና የሚሆኑት። የተሰጣችውን መድረክ በመጠቀም ወጣቱን የሚያሳስቱና፣ የሾለና ሳይንሳዊ አስተሳሰብ ኖሮት አገሩን በፀና መሰረት ላይ እንዳይገነባ የሚያደርጉ ናቸው። በተለይም የአገራችን የፖለቲካ እንቅስቃሴ ሳይንሳዊ ፈሩን ለቆ ከወጣ ከዛሬ አርባ ዐመታት ጀምሮ የሁሉም ትግል ስልጣንን በመጨበጥ ላይ ያተኮረ ስለሆነ በፖለቲካ ስም የተካሄደው ውዝግብ ሰፋ ላለ ምሁራዊ እንቅስቃሴና ሳይንሳዊ ክርክር አመቺ አልነበረም። ቡድናዊ ስሜትም ስላየለና ፖለቲካውም ይበልጥ በዘለፋና በጥላቻ ላይ የተመረኮዘ ስለነበር ስነ-ስርዓት ባለው መልክ ለመታገልና ወጣቱን ለማስተማር በፍጹም አልታቻለም። አብዮቱ ለአንዴም ለመጨረሻም ጊዜ ድምጥማጡ ጠፋ ከተባለ በኋላም አዲስ ምሁራዊ ኃይል ብቅ በማለት ወጣቱን ማስተማርና የበሰለ አስተሳሰብ እንዲኖረው ማድረግ አልተቻለም።  በመሆኑም ዕውነተኛ በሳይንስና በጥበብ ላይ የተመረኮዘ ኢትዮጵያዊ ስሜትን ማዳበር አልተቻለም። ዛሬም እንደትላንትናው ፊዩዳላዊ አሰትሳሰብ ከጥራዝ ነጠቅ የዘመናዊነት አስተሳሰብ ጋር በመዋሃድ ዕውነተኛ ኢትዮጵያዊ ስሜትን የሚያኮላሽ የመሳፍንት አገዛዝ ለማምጣት ደፋ ቀና እየተባለ እንደሆን እንመለከታልን።

ስለሆነም በአለፉት ሃያ አምስት ዓመታት እዚህና እዚያ የተደረገውን መጯጯህና ጠላት ነው በሚባለው ላይ ያነጣጠረውን ተቃዎሞ ስንመለከት፣ ሁላችንንም አንድ የሚያደርገን አንድ ነገር ብቻ ነው። ሁላችንም በወያኔ ላይ ከፍተኛ ጥላቻ አለብን። ይሁንና ግን ወደ ዝርዝር ጉዳዮች ላይ ስንመጣ የሚያለያዩንና የማንስማማባቸው አያሌ ጉዳዮች አሉ። አንደኛ ፣ ወያኔ እንዴት ስልጣን ላይ እንደወጣና በዚህ ዐይነቱ አገር አፍራሽ ፖለቲካው ማን ከበስተጀርባው እንዳለና፣ የሃሳብና የማቴሪያል ድጋፍም እንደሚሰጠው በመሀከላችን ስምምነት የለም። ቢታወቅም እንኳ በተለያዩ ምክንያቶች የተነሳ ስሙ እንዲነሳ አይፈለግም። እንዲያውም በአንዳንድ ተቃዋሚ ነን፣ የዚህ ወይም የዚያ ድርጅት የውጭ ፖለቲካ ተጠሪ ነን በሚባሉት ቃለ-መጠይቅ ሲጠየቁ የሚሰጡት መልስ ለወዳጅ አገሮች አስታውቀናል እያሉ ነው። ይህ ዐይነቱ አባባል በመሰረቱ የትግልን ዲያሌክቲክንና ሎጂክን በፍጹም አይመለከትም። አንድ የውጭ ኃይል ስልጣን ላይ ካለ አገዛዝ ጋር እጅና ጓንቲ ሆኖ የሚሰራ ከሆነና፣ አገዛዙ አገራችንን በማፍረስ ፖለቲካው እንዲገፋበት ማንኛውንም ዐይነት ድጋፍ የሚሰጠው ከሆነ ሎጂካሊ ሲታሰብ አንደኛው ወዳጅ፣ ሌላው ደግሞ ጠላት ሊሆን አይችልም። ስለሆነም ይህ ዐይነቱ እጅግ የተምታታና ከሳይንስና ከሎጂክ ጋር የማይጣጣም ትግል የሚባለው ፈሊጥ ለህዝባችንና ለአንድነታችን የሚደረገውን ትግል ዓላማ-ቢስ ያደርገዋል። በሁለተኛ ደረጃ፣ አገዛዙ እስካሁን ድረስ በተከተለውና በሚከተለው የኢኮኖሚ ፖሊሲ ላይና፣ ህዝባችንን ወደ ድህነት በገፈተረው የኒዎ-ሊበራል የኢኮኖሚ ፖሊሲ ላይ አንዳችም ስምምነት የለም። እንዲያውም በአብዛኛዎች አነጋገርና ግንዛቤ አሁንም ቢሆን በአገራችን ምድር በመንግስት የተደገፈ የኢኮኖሚ ፖሊሲ ነው የሚካሄደው እየተባለ ነው  የሚነገረን። ሀቁ ግን እነ አቶ መለስ ስልጣን ሲይዙ ከቀረበላቸው ቅድመ-ሁኔታዎች አንዱ የኒዎ-ሊበራል የነፃ ገበያ ኢኮኖሚን ተግባራዊ ማድረግ እንዳለባቸው ነው። በመሆኑም በእነ ዓለም አቀፍ የገንዘብ ድርጅትና(IMF) የዓለም ባንክ አማካይነት የዓለም አቀፍ ኮሚኒቲው ባዘዘው መሰረት የነፃ ገበያ ቅድመ-ሁኔታዎች ናቸው አንድ በአንድ የዋሉት። እነዚህ ደግሞ በተግባር ሲተረጎሙ ስትራቴጂክ የሆኑ የአገሪቱ ሀብቶች በአገዛዙና በእሱ ስር በተደራጀው ኤፈርት በሚባለው ድርጅት ቁጥጥር ስር ነው እንዲወድቁ የተደረገው። ይህ  ዐይነቱ በውጭ ኃይሎች ተዘጋጅቶ የመጣውና ተግባራዊ የሆነው የኢኮኖሚ ፖሊሲ ነው አገራችንን መቀመቅ ውስጥ የከታት።

በመሀከላቻን ያለው ትልቁ ችግር ትግል በሚባለው መድረከ ውስጥ ከዚህም ከዚያም የተሰባሰበ፣ የዚህ ወይም የዚያኛው ድርጅት አባል ወይም ደጋፊ የነበረ፣ ክፉም ሆነ ደግ ስራ የሰራ በአንድ የትግል መድረክ ውስጥ መካተታቸው ነው። ባለፉት ሃያ አምስት ዓመታትም የጭንቅላት ተሃድሶ ስራ ስላልተሰራ ትግል የሚባለው ፈሊጥ በመግበስበስ የሚካሄድ እንጂ በጠራ ርዕይ ዙሪያ ጥናት እየተጠና አይደለም። ስለሆነም አንዳንዱ በሚጠይቅበት ጊዜ የሚሰጠው መልስ ወያኔን ከመጥላት የሚያልፍ አይደለም። አብዛኛው ታጋይ  ወይም የአገር ተቆርቋሪ ነኝ ባይ፣ ትግሉ ይህንን ወይንም ያንን ድርጅት፣ ይህንን ወይንም ያንን ግለሰብ ከመደገፍና ከማምለክ የሚያልፍ አይደለም። ይህም ማለት እስከዛሬ ድረስ የሚካሄደው ትግል ህዝባችንን የስልጣኔ ባለቤት ለማድረግና አገራችንም በአካባቢው አገሮች ደግሞ ምሳሌ እንድትሆንና እንድትከበር ሳይሆን  ስልጣን ላይ ለመቀመጥና ለመታወቅ ብቻ የሚደረግ ትግል ነው ። ከዚህ ስንነሳ ትግሉ የአገር ወዳድነት ስሜት ይኑረው አይኑረው ለማወቅ በጣም የሚያስቸግር  ነው። መግበስበስ የበዛበት ትግል በመሆኑ ትግሉን መልክ ለማሲያዝና፣ ወዳጅና ጠላትን ለመለየት የማይቻልበት ሁኔታ ከተፈጠረ ረዘም ያለ ጊዜ ሆኗል ማለት ይቻላል።አንዳንዱ ግራ ይሁን ቀኝ፣ ፋሺስት ይሁን ሌላ፣ በአጭሩ  ምን ዐይነት ርዕዮተ-ዓለም እንደሚከተል የሚታወቅ ነገር የለም። ስለዚህም ሰፋ ወዳ አለና ወደ ተወሳሰበው የዓለም ሁኔታ ስንመጣ አብዛኛዎቻችን፣ በተለይም ደግሞ በተከታታይ ለድህረ-ገጾች የሚጽፉም ሆነ ተጋብዘው ንግግር የሚያደርጉ ኢትዮጵያውያን ስለዓለም ሁኔታና የዓለም ፖለቲካ፣ የሚሊታሪና የኢኮኖሚ አወቃቀር፣ እንዲሁም  በአገራችን ላይ ስለሚኖራቸው ተፅዕኖ የሚያስተምሩንና የሚነግሩን ምንም ነገር የለም። መሰረታዊ በሆኑ ጥያቄዎች ላይ ግልጽነት ከሌለ ደግሞ ለኢትዮጵያ ህዝብ ነፃነትና፣ እንዲሁም በሳይንስና በቴክኖሎጂ ላይ ለተመሰረተ ሰፋ ላለ ኢኮኖሚ መታገል በጣም አስቸጋሪ ይሆናል ማለት ነው።

እንደሚታወቀው እ.አ ከ1989 ዓ.ም ጀምሮ የዓለም የፖለቲካ፣ የሚሊታሪና የኢኮኖሚ ሁኔታ እጅግ እየተመሰቃቀለና፣ በተለይም አብዛኛዎቹ የሶስተኛው ዓለም አገሮችና ህዝቦቻቸው ከአቅማቸው በላይ እየሆነ መጥቷል። ኮሙኒዝም ከፈራረሰ በኋላ ብቸኛው ኃያል መንግስት እኔ ብቻ ነኝ የሚለው የአሜሪካን ኢምፔሪያሊዝም በሱ ቁጥጥር ስር ያሉ፣ የዓለም አቀፍን ስም የያዙ ኢንስቲቱሽኖችን መሳሪያ በማድረግ፣ በተለይም በአፍሪካ አገሮች ላይ ጫና በማድረግ ኢኮኖሚያቸውን ለማዘበራረቅ ችሏል። በነፃ ገበያ ስም አማካይነት ተግባራዊ የሆኑት የኢኮኖሚ ፖሊሲዎች በሙሉ፣ የተወሰነውን የህብረተሰብ ክፍል ሲያደልቡ፣ በሌላ ወገን ደግሞ ሰፊው ህዝብ ወደ ድህነት እንዲገፈተር ተገደደ። የውጭው ገበያ ክፍት በመሆኑ ከውጭ የሚገባው አዳዲስና በጠቀሜታ ላይ(Second hand goods)የዋሉ ዕቃዎች ከውስጥ የማመረት ኃይላቸውን አዳከሙ። በዚህም ምክንያት የተነሳ አዳዲስ የስራ መስክ መከፈት ቀርቶ፣ ራሱ ሰራተኛው ሲሰራ ከነበረበት በመባረር የስራ አጥ ለመሆን ተገደደ። ይህ በራሱ በትላልቅ ከተማዎች ውስጥ አዲስ ዐይነት የህብረተሰብ ቀውስ በመፍጠር፣ ተከታታይና ጥሩ ገቢ የሌለው ሰፊ ህዝብ በቆሻሻ  ቦታዎች(Slums) እንዲኖር ተገደደ። በሌላ ወገን ደግሞ አዳዲስ የሚሰሩት ህንፃዎችና የመኖሪያ ቤቶች ከተማዎቹ ውስጥ ካሉት የመብራትና የንጹህ ውሃ አቅርቦት ጋር እየተመጣጠኑ ባለመሰራታቸው በከፍተኛ ደረጃ ንጹህ ውሃንና ኃይልን በመጋራት ሰፊው ህዝብ ከፍተኛ ችግር ውስጥ እንዲወድቅ ተገደደ። ይህ ዐይነቱ ሁኔታ በተለይም በአዲስ አበባ ከተማ ውስጥ አፍጦ አግጦ ይታያል።፡በግሎባላይዜሽንና በነፃ ንግድ ስም ተግባራዊ የሆነው የኢኮኖሚ ፖሊሲ እንደምናየው አገራችን ከጥገኝነት ያላቀቀ ሳይሆን የባሰውኑ ዕዳ ውስጥ የከተተንና፣ ኢኮኖሚያችንን ያዘበራረቀ ነው። በዚህም ምክንያት የተነሳ አገራችን እንደ አገርና ህዝባችንም እንደ ህብረተሰብ እንዳይታይና ህልሙንና ፍላጎቱን ተግባራዊ ሊያደርግ የሚችልበት ሁኔታ እንዳይፈጠር ተደርጓል። የኢትዮጵያዊነት ትርጉሙም እየጠፋና ሰፊው ህዝብ እየተናቀና ተመጽዋች እየሆነ ለመኖር ተገዷል።

ይህ በቻ አይደለም፤ የአሜሪካን ኃያል መንግስት በቻይናና በአንዳንድ በኢኮኖሚ እያደጉ በመጡ አገሮች የበላይነቱን ላለመነጠቅ ሲል በአንዳድን አፍሪካ አገሮች ውስጥ የጦር ሰፈሩን በመዘርጋት፣ ብዙ የአፍሪካ አገሮች በጦርነት እንዲታመሱ እያደረገ ነው። በዚህም ምክንያት የተነሳ አገዛዞች ሽብርተኝነትን ለመዋጋት ቅድሚያ መስጠት አለባቸው በማለትና መኮንኖችን በማሰልጠን የብዙ አፍሪካ መንግስታትን አትኩሮ ወደ ጦርነት እንዲያዘነብሉ ማድረግ ችሏል። ለኢኮኖሚ ዕድገትና ለማህበራዊ ፕሮጀክቶች ሊውሉ የሚችሉ ሀብቶች በዚህ ዐይነቱ አሳሳቸ ፖሊሲ አገሮች እየወደሙ ናቸው። የወያኔ አገዛዝም በዚህ ዐይነቱ የፀረ-ሽበርተኝነት ፖሊሲ በመካተት ይኸው እንደምናየው ራሱን ማጎልመሱ ብቻ ሳይሆን የሰው አገር ድንበር ጥሶ በመሄድ አገራችን ተወዛግባ እንድትኖር አላስፈላጊ ሁኔታዎች ፈጥሯል።

በመሰረቱ እነዚህ ከላይ አጠር መጠን ባለ መልክ የዘረዘርኳቸው ጉዳዮች የፖለቲካ ፓርቲዎችና በየጊዜው በየተሌቪዠኑ እየቀረቡ ገለጻ የሚሰጡ፣ ወይም ስለ ዓለም ፖለቲካ የጥያቄና መልስ ምልልስ የሚያደርጉ ግለሰቦችና ድርጅቶች ተግባሮችና ግዴታዎች ነበሩ። እንደማየውና እንደምከታተለው ከሆነ ጋዜጠኞችም ሆነ ራሳቸው ተጠያቂዎቹ በዓለም ላይ ምን እንደሚካሄድ የማያውቁ ይመስል የሚጠይቁትና የሚሰጡትም መልሶች ከተጨባጩ የዓለም ሁኔታ ጋር በፍጹም የሚጣጣም አይደለም። ሁኔታው በዚህ መልክ የሚቀጥል ከሆነ ጋዜጠኞችም ሆነ ራሳቸው ተጠያቂዎች በብዙ ሺህ የሚቆጠር ወጣትን በማሳሳት የኢትዮጵያዊነት ስሜት ደብዛው እንዲጠፋ ለማድረግ ይችላሉ። ዕውነተኛ የአገር ወዳድ ስሜትነት እንዳይዳብር በማድረግ ይህንን ወይንም ያኛውን ኃያል መንግስት እየተለማመጠ የሚኖር ትውልድ እንዲኮተኮትና የስልጣኔውም መንግድ እጅግ አስቸጋሪ እንዲሆን መንገዱን ሁሉ ያመቻቻሉ።

ስለሆነም የኢትዮጵያ ጠንቆችና ኢትዮጵያዊነትን የሚቀናቀኑ አስተሳሰቦችና የትግል ዘዴዎች ናቸው የምላቸው ነገሮች አብዛኛውን ጊዜ ዋና ምክንያታቸው በሰፊውና በሎጂካዊ መንገድ ካለማሰብ የመነጩ ናቸው። አብዛኛዎቻችን አንድ ወጥ አመለካከት አዳብረናል። አገርን በመገንባትና በማፍረስ መሀከል የተደረገውን በውስጥና በውጭ ኃይሎች መሀከል ያለውን የተወሳሰበ ትስስር ለማየትና ለመተንተን የምንችልበት መሳሪያ ያለን አይመስለኝም። በተለይም የተለያዩ ምሁሮች በአንድ ነገር ላይ ለምን የተለያየ አመለካከት ሊኖራቸው ይችላል ብለን ጥያቄ ስለማናቀርብ ነገሩን በመናቅና በመናናቅ መሀከል ያለ፣ ወይም ያለመስማማት ችግር አድርገን እንወስደዋለን። በመሰረቱ በሁለት ሰዎች ወይም በተለያዩ ድርጅቶች መሀከል ስምምነት ሊኖር የማይችለው አንድን የህብረተሰብ ሁኔታ በተለያየ መልክ ስለሚተረጉሙትና የተለያየ መልስ ለመስጠት ስለሚፈልጉ ነው። ወደ አገራችን ስንመጣ ያለው ችግር ግን በመሰረቱ አንድን የህብረተሰብ ታሪክ ለማንበብ የሚያስችለን አስተሳሰብ ወይም ስልት(School of Thought) ለማዳበር ያለመቻላችን ነው። አብዛኛዎቻችን በምን ዐይነት ቲዎሪ እንደምንደገፍና አንድን ተጨባጭ ሁኔታ እንዴት አድርገን ማንበብ እንዳለብን የተገነዘብን አይመስለኝም። ካለቲዎሪ ተግባር ስለማይኖር፣ በጭፍኑ የሚደረግ ትግል ወደ አጉል ግብግብና ጥፋት ያመራናል።

ስለዚህም ለኢትዮጵያ ጠንቅ የሆኑ ነገሮች፣ 1ኛ) የሃሳብ ጥራት አለመኖር፣ 2ኛ) በአንዳች ዐይነት ርዕይ አለመመራት፣ 3ኛ፟) የሃሳብ ጥራትና ርዕይ ሳይኖር ይህንን ሆነ ያንን ድርጅት በመከተል ወደ ጠብ ማምራት፣ 3ኛ) ለመደማመጥ ያለመቻል፣ 4ኛ) በፕሪንሲፕል አለመመራትና ለህሊና ለመገዛት አለመቻል፣ 5ኛ) ለአገር ዕድገትና ስልጣኔ የሚደረገው ትግል ከፍተኛ ዕውቀትን እንዲመጠይቅ ለመገንዘብ አለመሞከር፣ 6ኛ) ስለሆነም በዕድገት ስም የሚምል ወይም ተማርኩ የሚል ሁሉ ስለ ዕድገት አንድ አንድ ዐይነት አመለካከት ሊኖረው እንደማይችል ለመረዳት አለመሞከር፣ 7ኛ፟) ይህንን በሚመለከት በምሁራን ዘንድ የተደረገውን ሰፋ ያለ ትግልና ክርክር ለማወቅ አለመጣር፣ 8ኛ) የፖለቲካን ትርጉም ለመረዳት ያለመቻል፣ 9ኛ) የዓለምን የፖለቲካ፣ የሚሊታሪና የኢኮኖሚ አወቃቀር በየዋህነት መነጽር መመልከት 10ኛ፟) አሳሳች ኃይሎችን ለማወቅ ጥረት አለማድረግና ዝም ብሎ እነዚህ ወዳጃችን ናቸው፣ ይረዱናል ብሎ ዝም ብሎ በጭፍን ዕምነት መጓዝ… ወዘተ. እነዚህና ሌሎች አያሌ ነገሮች ለአገራችን ዕድገትና ሰላም ለሚደረገው ሰፊው ህዝባችን  እንቅፋት በመሆን ተብትበውን ይዘዋል።   ጤናማ የሆነ በሰብአዊነትና በዲሞክራሲያዊ መሮሆች ላይ የተመረኮዘ የኢትዮጵያዊነት ስሜት እንዳይዳብር ያግዱናል። ከድህነት እንዳንላቀቅና ዘለዓለማችንን ተመጽዋች ተቀባይ እንድንሆን ያደርጉናል። ባጭሩ የሳይንስና የቴክኖሎጂውን መንገድና ለሁለ-ገብ የሚደረገውን በራስ ላይ የመተማመንን ትግል ያግዱብናል፤ ዘለዓለማችንን በጨለማ ዓለም ውስጥ እንድንኖር ያደርጉናል።

 

የብሄረሰብ ጥያቄ አፈታትና የፌዴራሊዝም ጉዳይ !

ለሁላችንም ግልጽ መሆን ያለበት ጉዳይ የብሄረሰብን ጥያቄ በክልል እየከለሉ ችግሩን መፍታት በፍጹም አይቻልም። ከላይ ደረጃ በደረጃ ለማሳየት እንደሞከርኩት መስረታዊ ጥያቄ የተገለጸለት ዲሞክራሲያዊ ኢንስቲቱሽንና የፖለቲካ ጥበብን የተካነ መደብ አለመኖሩ ነው ያለውን መጠነኛ አለመግባባት ሊያባብሰው የቻለውና የሚችለው። በተለይም ያልተገለጸለትና ዲሞክራሲያዊ ያልሆነ ኢንስቲቱሽንና የገዢ መደብ ከውጭ ኃይሎች ጋር በመቆላለፍ ማንኛውንም አገር አፍራሽ ፖሊሲ የሚያካሄድ ከሆነና የጦር ሰፈርም በመስጠት በአካባቢው ሰላም እንዳይኖር የሚያደርግ ከሆነ  ለብሄረሰብ ነፃነት እንታገላለን የሚሉ ኃይሎች ነገሩን ሊያባብሱት ይችላሉ። ከእንደዚህ ዐይነቱ አስቸጋሪ ሁኔታ መውጣት የሚቻለው በሁሉም ነገሮች ላይ ግልጽ የሆነ ውይይትና ጥናት ሲካሄድ ብቻ ነው። በፍልስፍናና በሳይንስ ዙሪያ ግልጽ አቋም መያዝ የተቻለ እንደሆነና፣ የነፃነት ጉዳይ ሁሉንም የህብረተሰብ ክፍል የሚመለከት መሆኑን ግንዛቤ ከተደረሰበት በቀላሉ መፍትሄ መስጠት ይቻላል።

በመሰረቱ የአንድ ብሄረሰብም ሆነ ህዝብ ጥያቄ በመጀመሪያ ደረጃ መሰረታዊ ነገሮችን፣(Basic Needs) ማለትም፣  የተስተካከለ ምግብ፣ ንጹህ ውሃ፣ መጠለያ ማግኘት፣ ህክምናና ትምህርት ቤት ማግኘት ናቸው። እነዚህ ነገሮች የማንኛውም ህዝብ ጥያቄዎችና ከመብትም ጋር በጥብቅ የሚተሳሰሩ ናቸው። ማንኛውም ብሔረሰብ ሰው እንደመሆኑ መጠን፣ ለመኖር፣ ለማሰብና ለመስራት ይችል ዘንድ በየጊዜው ተመጣጣኝ ምግብ ማግኘት አለበት። እንዲዚሁም ንጹህ ውሃ ማግኘት አለበት። የለም መጀመሪያ መብትህን ማግኘት አለብህ፤ ለዚህም የራስህን ዕድል በራስህ ለመቀዳጀት ከፈልግህ ታጋል የሚባል ከሆነ አንድ ህዝብ ዕውነተኛ ነፃነቱን እንዳይቀዳጅ እንደማድረግ ይቆጠራል። በተለይም በአውሮፓ የህብረተሰብ ታሪክ ውስጥ የብሔረሰብ ጥያቄ እንደመታገያ መሳሪያ ሆኖ ተወስዶ አይታወቅም። በአውሮፓ የትግል ታሪክ ውስጥ ቅድሚያ የተሰጣቸው ጭንቅላትን የሚያዳብሩ የፍልስፍናና የተፈጥሮ ሳይንስ እንዲሁም ቋንቋን ማበልጸግና በማዳበር ላይ ያተኮረ ነበር። በሁሉም አገሮች የተለያዩ ቋንቋዎች ይነገሩ ነበር። ይህ አካሄድ አለመግባባትን በመፍጠሩና፣ ለዕድገትም እንቅፋት በመሆኑ የግዴታ አንድ ቋንቋ መፍጠርና ማዳበር ተቻለ። በዚህ አማካይነት  በአጭር ጊዜ ውስጥ ስልጣኔ መቀዳጀት ተቻለ። ወደእኛ አገር ስንመጣ ግን የተያዘው የዳበረውን የግዕዝና የአማርኛ ቋንቋ በማጥፋት ሁሉም አዲስ በተፈጠረለት አዲስ ፊደልና በቋንቋው እንዲነጋገር በማድረግ ህዝቡ ጭንቅላቱን እንዳይከፍትና እንዳይፈጥር ማድረግ ነው። በተለይም የቋንቋ ምሁራን ነን የሚሉ የእንግሊዝ ሰላዮች በአገራችንና በተለያዩ የአፍሪካ አገሮች በመሰግሰግ አደገኛ ስራ እየሰሩ ነው። በውጭ ጉዳይ ሚኒስተር ውስጥ የተሰገስጉ የእንግሊዝ ሰላዮችና ትላልቅ ህንፃዎች በመገንባት በዕርዳታ ስም የሚዘባነኑት ዋና ተልዕኮአቸው  ብሄረሰብን ከብሄረሰብ ማጋጨትና በተለያዩ የሃይማኖት ተከታዮች መሀከል መፋጠጥ እንዲኖርና የርስ በርስ ጦርነትም እንዲከካሄድ ማድረግ ነው። ለሁሉም ህዝብ ደህንነትና ለአገራችን ዕድገት እታገላለሁ የሚል ሁሉ ይህንን የተመሰጣጠረ ሁኔታ ጠጋ ብሎ መመልከትና መመርመር አለበት። በየዋህነት እዚህና እዚያ የሚደረገው መሯሯጥ የመጨረሻ መጨረሻ ገደል ውስጥ ነው የሚከተን።

ሰለዚህም የችግሩ አፈታት ከዲሞክራሲያዊ ሁኔታዎችና ቀስ በቀስ ብቃትነት ያላቸው አገር አቀፋዊ እንስቲቱሽኖች ከመቋቋማቸው ጋር የተያያዘ ነው። ብሄረሰብን በክልል አካልሎ ፌዴራላዊ አገዛዝ ነው ያለው ማለት ቀልድ ነው። በመጀመሪያ ደረጃ ፌደራላዊ አወቃቀር ከሪፑብሊካዊ አስተሳሰብና አገዛዝ ጋር የተያያዘ ነው። በሌላ አነጋገር የአንድን ግለሰብም ሆነ የአንድን ደርጅት ዲስፖታዊ አገዛዝና ሬሶርስን መቆጣጠር የሚቃወም ነው። ሪፑብሊካዊ አገዛዝ የግለሰብ ነፃነቶችንና ከዚህ ጋር የተያያዙ ማንኛውም መብቶችን፣ ማለትም የፕሬስ ነፃነትና በነፃ መደራጀትንና ሃሳብን መግልጽ የሚያከብር ነው። ሪፑብሊካዊ አወቃቀር በገዢው መደብና በመንግስት መኪና መሀከል ያለውን ልዩነት ቁልጭ አድርጎ የሚያስቀምጥና፣ የመንግስት ኢንስቲቱሽኖች የአንድ የገዢ መደብ የግል ሀብት እንዳልሆኑ የሚያረጋግጥ ነው። በመሆኑም በህግ አውጭው፣ አጽዳቂውና አስፈጻሚው መሀከል የስራ ክፍፍል መኖር አለበት። አንድ የገዢ መደብ በህግ አስከባሪ ፍርድ ቤት ውሳኔ ውስጥ መግባት የለበትም። ይህ ሲሆን ብቻ ወደ ፊዴራሊዝም ስርዓት ለማምራት ይቀላል።

በመሰረቱ የፌዴራላዊ ስርዓት አወቃቀር ሀብትን ለማንቀሳቀስና ለዕድገት የሚያመች ነው። በማዕከላዊ አገዛዝ አማካይነት ተግባራዊ ሊሆን የማይችለው ዕድገትና ከዚህ ጋር የተያያዙ እንስቲቱሽናዊ ለውጦችና መሻሻሎች ተግባራዊ ሊሁኑ የሚችሉት አንድ አገር በፌዴራል ደረጃ ስትዋቀር ነው።  ይህ ብቻ ሳይሆን፣ በክፍለ-ሀገሮች መሀከል ውድድር እንዲኖር በማድረግ ዕድገትን ያፋጥናል። ይሁንና ግን አንድን አገር በፌደራል ደረጃ ማዋቀር የግዴታ በየቦታው የተገለጸለትና የማሰብ ኃይሉ ከፍተኛ የሆነን አገዛዝንና የተማረ የሰው ኃይልን ይጠይቃል። እንደ አገራችን ባለ ሁኔታ ውስጥ በክልል ደረጃ የሚዋቀር ፌዴራልዝም የግዴታ ወደ ዋር ሎርድነት የሚያመራና ዕድገትን የሚቀናቀን አካሄድ ይሆናል ማለት ነው። በየክልሉ ተዋቀሩ የተባሉት የፌዴራሊዝም አስተዳደሮች በሙሉ በምንም ዐይነት ፊዴራሊያዊ የሚያሰኛቸው አይደሉም። በአጠቃላይ ሲታይ በአንድ ዲስፖቲያዊ አገዛዝ ቁጥጥር ስር ያሉና ባስፈለገበት ጊዜ ጣልቃ በመግባት በኗሪው ላይ ጦርነት የሚያውጅ ነው። በየቦታው የሚካሄዱትም  የልማት ክንውኖች በሙሉ አገራችንን ወደ ማዕከለኛው ዘመን በፍጥነት እንድትጓዝ  ያደረጉ እንጂ ሰፊውን ህዝብ ከድህነት ያላቀቁና ስርዓት ያለው ኑሮ እንዲኖር ያደረጉ አይደሉም።

ክዚህ ሁሉ አስቸጋሪ ሁኔታ ለመውጣት ቀደም ብዬ ባለፈው ጽሁፌ ላይ ለማሳየት እንደሞከርኩት በመጀመሪያ ደረጃ ከሁሉም ብሄረሰቦች የተውጣጡ ግለሰቦች የሚሰለጥኑበት ኢንስቲቱሽን ማዋቀርና እዚያው ውስጥ ገብተው እንዲማሩ ማድረግ ችግሩን ሊፈታው ይችላል ብዬ አምናለሁ። በመሰረቱ በአገራችን ያለው ችግር የብሄረሰብ ጥያቄ አለመፈታት ጉዳይ አሁንም አገራችን ፊዩዳላዊ ወይም ያልተገለጸለት አስተሳሰብ ባላቸውና ኋላ-ቀር በሆኑ እንስቲቱሽኖች መተዳደሯ ነው። በዚህም ምክንያት የተነሳ ህዝባችን እንዳይማርና እንዳያውቅ ተደርጓል። ርስ በርሱ እንዲጠራጠር ሆኗል። ይህንን ችግር ለመፍታት የሚቻለው ከኤሊት ትምህርት ባሻገር አጠቃላይ የሆነ የማስተማር ዘመቻ ሲካሄድ ነው። በቅርቡ በሁለት የዲሞግራፊ ፕሮፌሰሮች አማካይነት ተጽፎ ለንባብ ከቀረበ መጽሀፍ መገንዘብ የሚቻለውና ብዙ ጥናቶችም የሚያረጋግጡት ለአንድ አገር ችግር ዋው መፍትሄ ሰፊውን ህዝብ ያካተተ ትምህርትና ሰፋና ጠለቅ ያለ ዕውቀት አስፈላጊ እንደሆኑ ነው። ከዚህ ስንነሳ የብሄረሰቦች ችግር እየተባለ የሚጠራውንና እንደ ጊዜ ቦንብ ሆኖ የሚፈራውን ችግር መፍታት የሚቻለው በዕውቀትና በተስተካከለ ዕድገት አማካይነት ብቻ ነው። በሌላ ወግን ግን ከዛሬ የክልል ፌደራሊዝም ይልቅ በክፍለ-ሀገር ደረጃ የዋቀረ ለስራና ሀብትን ማንቀሳቀስ የሚያመች ፊዴራላዊ አወቃቀር ቢዘረጋ ለዕድገት በጣም ያበጃል። በየክፍለ-ሀገራት የሚዋቀረውም አስተዳደር በዕውቀትና በችሎታ ሲሆን እንደ ቋንቋ የመሳሰሉትን ነገሮች በቀላሉ መፍታት ይቻላል። ያም ሆኖ የአማርኛ ቋንቋና ወደፊት ደግሞ ግዕዝ ብሄራዊ ቋንቋ ብቻ ሳይሆኑ የሳይንስና የፍልስፍና መማሪያዎች ሆነው መዳበር አለባቸው። እነዚህን በማዳከምም ሆነ በመከልከል ዕድገትን መቀዳጀት አይቻልም። እነዚህ ሁለቱ ቋንቋዎች በሁሉም ነገር የዳበሩና ለሳይንስና ለቴክኖሎጂ የሚያመቹ ናቸው። አሁን በቅርቡ በፊዚክስና በማቲማቲክስ በሰለጠኑ ኢትዮፕያውያን ፕሮፌሰሮች ከአማርኛ፣ ከግዕዝ፣ ከኦሮሞኛና አንዳንድ የእንግሊዘኛ ቃላት ታኮሎበት ለመማሪያ የቀረበው መጽሀፍ የሚያረጋግጠው በአገራችን ሁሉም የትምህርት ዐይነት በዚህ መልክ ቢቀርብ ለዕድገት ማምችቱ ብቻ ሳይሆን ለመግባባትና ሃሳብ ለሃሳብ ለመለዋወጥ በጣም ያመቻል።

ያም ሆነ ይህ ማካሄድ ያለብን ፖለቲካ ጥበብ የተሞላበት መሆን አለበት። የችግሩን መንስኤ በሚገባ መመርመር አለብን። ለመብታችን እንታገላለን የሚሉትን የዚህም ሆነ የዚያኛውን ታጋዮች ሁሉ እንደተገንጣይና እንደ አገር በታታኝ አድርገን መመልከት የለብንም። ያለውን ችግር ከሳይንስ አንፃር እንዴት እንደምንፈታው ቁጭ ብሎ ማጥናትና መወያየት ያስፈልጋል። በሌላ ወገን ደግሞ ሌሎች አንድነትን ይቀናቀናሉ ብለን ከመጻፉችንና ከማውራታችን  በፊት የአገር አንድነት እንዲጠበቅና በህዝብ መሀከል መተማመን እንዲኖር ምን ምን ነገሮችን ሰራን ብለን ራሳችንን መጠየቅ አለብን። እንደሚታወቀው ለዛሪይቱ ኢትዮጵያ በዚህ ዐይነቱ እጅግ አስቀያሚ ሁኔታ ላይ መገኘት ሁሉም የየበኩሉን አስተዋፅዖ አድርጓል። ግራ ነኝ ከሚለው ጀምሮና ከቢሮክራሲውና ከአሪስቶክራሲው ወገን የተወለደው ሁሉ፣ ሁሉም በየፊናው ለዛሬይቱ ኢትዮጵያ በዚህ ሁኔታ ላይ መገኘት  የየበኩሉን በየፊናው አስተዋፅዖ አበርክቷል። አብዛኛው ባለማወቅ ሲሆን፣ ጥቂቱ ደግሞ የራሱን የኢኮኖሚና የሶሻል ስታተስ ለመጠበቅ ሲል አሻጥር መስራቱና ከኢምፔሪያሊስት ኃይሎች ጋር ማበሩና ለመበታተን የሚያመች ኢንፎርሜሽን ማቀበሉ ኢትዮጵያን አዳክሟታል፤ ለዚህ ዐይነቱ ግራ የገባው አገዛዝ ሁኔታውን አመቻችቶ ሰጥቷል።

ለመቋጠር ያህል፣ የኢትዮጵያ አንድነት ሊጠበቅ የሚችለው የህዝቡ ኑሮ ሲሻሻል ብቻ ነው። ከድህነትና ከስንዴ ልመና ሲላቀቅ ብቻ ነው። በአዲስ የዕድገት ጎዳና በአንድነት ተነሳስቶ አገሩን ለመገንባት ሲንቀሳቀስ በቻ ነው። የኢትዮጵያ አንድነትና ህዝባችንም የሚከበረው የሳይንስና የቴክኖሎጂ ባለቤት መሆን ሲቻል ብቻ ነው። ሰፋ ያለ የስራ ክፍፍል፣ ቆንጆ ቆንጆ ከተማዎችና መንደሮች፣ እንዲሁም ጠቅላላውን አገሪቱን የሚያዳርስና አንዱን ክፍለ-ሀገር ከሌላው የሚያገናኝ፣ ከተማን ከገጠሩና ከመንደሩ ጋር የሚያይዝ የመገናኛና የመመላለሻ የባቡር ሃዲድ ሲዘረጋ የዚያን ጊዜ ሁሉም ጠብመንጃ ማንሳቱን ያቆማል። ሁሉም በየፊናው ሆዱን ለመሙላትና ቤት ለመስራትና ልጆችም ለመውለድና ለማሳድገ ደፋ ቀና ማለት ይጀምራል። አሁንም ለአንድነትና ለኢትዮጵያዊነት በሳይንስና በቴክኖሎጂ ላይ የተመሰረተ ሁለ-ገብ(Holistic) የኢኮኖሚ ግንባታ እጅግ አስፈላጊ ነው። ከዚህ ውጭ ማሰብና በየፊናውና በቡድን ቡድን መደራጀቱና አሳሳቾችን እየጋበዙ የሆነ ያልሆነውንና፣ ከሳይንስ ውጭ የሆነ ነገር ንግግር እንዲያደርጉ ማድረግ የድህነቱና ያለመረጋጋት ዘመኑን ያራዝማል። ስለሆነም የውስጥ ለውስጥ ጨወታዎች መቅረት አለባቸው። ሁሉም ነገር ለሳይንስ፣ ለፍልስፍናና ለቴክኖሎጂ የሚለው አስተሳሰብ በሁላችንም ጭንቅላት ውስጥ መቀረጽና ተግባራዊ መሆን አለባቸው። በሌላ ወገን ግን ለብሄረሰቤ ነፃነት እታገላለሁ የሚለው ግለሰብም ሆነ ድርጅት ቆም ብሎ ራሱን መጠየቅ አለበት። እጅግ በተሳሰረና በብዙ ችግሮች በተወጠረ ህብረተሰብ ውስጥ እንዴት አድርጎ እሱ የሚለውን የብሄረሰብ ነፃነት ተግባራዊ እንደሚያደርግና ይህም ምን እንደሚምስል በዝርዝር ማስረዳት አለበት። ካለበለዚያ የብሄረሰቦች ጭቆና ሰፍኗል እያሉ ማራገቡ ብቻ የትም ሊያደርሰን አይችልም። ችግሩ የአንድ ወይም የሁለት ብሄረሰብ ችግር ብቻ አይደለም በአገራችን ምድር የሰፈነው። በአገራችን ምድር የሰፈነው ፀረ-ዲሞክራሲያዊ ስርዓትና ጭቆና እንዲሁም ድህነትና ኋላ-ቀርነት ከዘጠና በመቶ በላይ የሚሆነውን ኢትዮጵያዊ ሁሉ የሚመለከት ነው። ችግሩ የአማራም የኦሮሞም ሆነ የጠቅላላው ብሄረሰብ ችግር ነው። ችግሩ የቋንቋ ሳይሆን የነፃነት እጦት ነው። መሰረታዊው8 ጥያቄ ሁሉንም ነገር ሊያካትት የሚችል ሰፊ የዕድገት እጦት ጥያቄ ነው።             

       ፈቃዱ በቀለ                 fekadubekele@gmx.de

ታሪካዊው የጎንደር ሰልፍ እና እንድምታው –ክንፉ አሰፋ

$
0
0

በሰሞነኛው የአዲስ አቤ ቀልድ ልጀምር። ወጣቱ፣ ሱሪ ለመግዛት ወጥቶ አንድ የልብስ ሱቅ ወስጥ ገባ። ባለ ሱቁ ጠየቀው። “የቻይና ይሁንልህ ወይንስ የአውሮፓ ሱሪ?”  ወጣቱም መለሰ። “የለም የለም… የጎንደሩን ሱሪ ነው የምፈልገው።”

 Gonder6
እስረኞችን የማስፈታቱ ሰላማዊ ጥያቄ የእብሪት መልስ ሲያገኝ፤  ጨዋታውም ተቀየረ።   “እንዲያውም አናውቅህም። ከህዝብ ጫንቃ ላይ ወረድ” ሲል ነበር የጎንደር ሕዝብ ብረትን ሰብሮ ዙፋኑን የነቀነቀው። “ወንዱን በምርቃና ሴቱን በቃና አደንዝዘን ይዘነዋል!” ያሉት ሕዝብ ከቶውንም እንዳልተዘናጋ አሳየን…. የመናገር እና ሃሳብን ያለፍርሃት የመግለጽ መብትን ህወሃት ሲፈልግ የሚሰጥ ሲያሻው ደግሞ የሚነፍገው የግል ሃብቱ አድርጎ ለ25 አመታት ሰንብቶ ነበር። ይህ መብት በኢትዮጵያ ሰንደቅ አላማ አሸብርቆ ጎንደር ላይ ተከበረ። በባህርዳር፣ በደሴ፣ በኦሮምያ፣ በመቀሌ…. ላይም ይቀጥላል..

           ከአርባ አመት በፊት የቬትናም ህዝብ ባዕዳን ያነገሱትን አሻንጉሊት መንግስት በሃይል ሲነቀንቀው፤ አሻንጉሊቱ ስርዓት ለሕዝብ እጅ ከመስጠት ውጭ አማራጭአልነበረውም። የህዝብ ያልነበረው ይህ መንግስት ወደ አመሻሹ ላይ ካመሸገበት የአይጥ ጉድጓድ ሆኖ መግለጫ ሰጠ። እንዲህ ሲል፣

           “ስልጣኑን ለህዝብ ለማስረከብ ከንጋት ጀምሮ እየጠበቅኩ ነው።…“

          የሰሜኑ ህዝብም ምላሽ የተጠበቀው ነበር፣  “ይህን ለማድረግ ትንሽ ዘገየህ።የሌለህን ስልጣን እንዴትስ ልታስረክብ ትችላለህ?…“

          ይህ ተላላኪ መንግስት ወድቆ የነበረው ከህዝባዊው አመጽ እና እንቢተኝነት በፊት መሆኑን አላስተዋለውም። ስርዓቱ የወደቀ ራሱ ያወጣውን ህግ ራሱ ሲሽረውነበር። ሕዝብ “መንግስት የለም!” ማለት የጀመረው ለአፋኝ አዋጆች አልንበረከክም ብሎ አደባባይ በወጣ ግዜ ነበር።  ይህ መንግስት የተወገደውም ለዜጋው የመብትጥያቄ የጥይት ምላሽ በሰጠ ግዜ ነው።

          “የዘመናችን ትልቁ ክስተት!”  ብሎታል የኩባው ፊደል ካስትሮ።

          ባለፈው እሁድ በጎንደር የታየው የሕዝብ እንቢተኝነትም የዘመናችን ትልቁ ክስተት ነበር። ሕዝብ የተፈጥሮ መብቱን ተነጥቆ በጫንቃው ላይ ተጭኖ የነበረውንቀንበር ያስወገደበት ክስተት!  ስልጣን የህዝብ እንጂ የጥቂቶች መፈንጫ አለመሆኑ የታየበት ክስተት። በኢትዮጵያ ታሪክ ላይ ወርቃማ አሻራ ጥሎ ያለፈ፤ ለሀገር የፍቅር፣ለዜጎች የፍትህ እና የህብረት ሃውልትን የተከለ ክስተት። የማይቻል የሚመስለውን ተራራ ደርምሶ የናደ ሃይል ስለነበር ታሪክ ይህንን ሰልፍ ይዘክረዋል።

          ግዙፉ የጎንደር ሕዝብ ሰላማዊ ሰልፍ እንደተተናቀቀ፣ የህወሃት መገናኛ ብዙሃን የሆነው ፋና ራዲዮ ሲዘግብ፤

          “የጎንደሩ የተቃውሞ ሰልፍ በሰላም ተጠናቀቀ።…” ነበር ያለው። “ጋዜጠኛው” ከምጥ እንደተገላገለች ሴት በረጅም ተነፈሰ።   በስፍራው ያልነበረው መገናኛብዙሃን በስፍራው የነበረውን ክስተት ሲደሰኩር፣ ለሰላማዊ ሰልፍ ፍቃድ የተከለከለ ህዝብ በራሱ ፈቃድ መውጣቱን፤ በሰልፉም ላይ እነሱ የከለከሉትን ባንዲራ ብቻመያዙን ጨምሮ አበሰረ።

          ይህንን የዜና እወጃ ያዳመጠው የጎንደር ሕዝብ  “ይህን ለማድረግ ትንሽ ዘገየህ።… “  ሳይለው አልቀረም።  ልክ እንደ አሻንጉሊቱ የቬትናም መንግስት፣የህወሃት የአፈና ግዜ ማብቃቱን እያረጋገጡት ይመስላል። አንድ ስርዓት መንግስትነቱ የሚያከትመው ራሱ ያወጣውን ህግ ራሱ ሲረግጠው እና ሕዝብም ለሱ አዋጅ ተገዥ አለመሆኑን ሲያሳየው ነው።  አላስተዋልነው ይሆናል እንጂ ህወሃት እድሜውን ጨርሶ በባከነ ሰዓት እንደሚንገዳገድ “የልማቱ” ተጠቃሚዎች ሳይቀሩነግረውን ነበር።  እነ ፃድቃን ገ/ትንሳኤ እና አበበ ተ/ኃይማኖት (ጆቤ) ከማጀታቸው ወጣ ወጣ ብለው አገሪቱ እጅግ አሳሳቢ ሁኔታ ላይ እንደምትገኝ፣ መንግስት በሚባለው እና በፓርቲ መሃል እንኳን ልዩነት እንደጠፋባቸው ነግረውናል።  ይህ ጉዳይ ጻድቃንን ግራ ካጋባው ሌላው ምን ይበል? ጆቤ የህወሃት ሙስና እና የፍትህእጦት ካስፈራው ተራው ህዝብ ምን ይሰማው?  የሚገርመው ነገር፣ እያየነው ያለው ቀውስ  የነ ፃድቃን እና የነ ጆቤ “ሌጋሲ”ም ጭምር መሆኑ ነው።

          የጎንደሩ አመጽ ሁለት አበይት ነገሮችን ጥሎልን አልፏል። አንደኛው መተባበር እና መደጋገፍን ማስተማሩ ነው::  አፍንጫ ሲመታ አይን ያለቅሳል እንዲሉ፤ በተለይ የኦሮሞ ወገናችን ደም የሁላችንም ደም ነው ማለታቸው የህወሃትን ከፈፍሎ መግዛት እቅድ የሚያፈርስ መፈክር ነበር።  የአኙዋክ መገደል ከአማራው መገደልተለይቶ አለመታየቱን፣ የሲዳማው ሰቆቃ.. የሁሉም ወገን ስእቆቃ እንደሆነ… የሚያሳይ ትእይንት ነበር። በማን አለብኝነት የሚጫኑ አዋጆችን መስበር መቻሉ ደግሞስልጣን ዛሬ በህዝብ እንጂ በአንባገነኖች እጅ አለመሆኑን አሳይቶናል። ሕዝብ በነቂስ ወጥቶ ለመብቱ ፈቃድ እንደማያስፈልገው ብቻ ሳይሆን ይልቁንም ጥንት አባቶቹ በአደራ ያስረከቡትን ባንዲራ ይዞ በመውጣቱም የስርዓቱን ማክተም አሳይቶናል።

          የማይነካ የመሰለው ጉልበቱ ሲፈታ፣ የማይሰበር የመሰለው ሃይል ሲሰበር ይህ የመጀመርያው አይደለም። በዘረፉት ሃብት እና በሰራዊታቸው ጉልበት ብቻእየተማመኑ የገዛ ወገናቸውን ሲበድሉ የኖሩ አንባገነኖች ከቶውንም መቶ አመት ሲቆዩ አላየንም። በአለማችን የተነሱ ብርቱ የሚባሉ አንባገነኖች በህዝብ ሃይልእየተዋረዱ መውደቃቸውን የታሪክ መዛግብት ይመሰክራሉ።

          የማያልቅ መንገድ እና የማይነጋ ጨለማ የለም። በአንጻሩ የማይመሽ ቀን የለም። የብዙዎ አንበገነኖች ችግር በጉልበታቸው ብቻ በመተማመን ዙፋናቸውንዘላለማዊ ለማድረግ ማሰባቸው ነው።   በዚህች ተለዋዋጭ አለም ውስጥ ለውጥ  የሰው ልጅ ፍላጎት ብቻ ሳይሆን ግደታም ነው። ዘገምታኛም ይሁን ቅጽበታዊ፣ እኛምበተራችን ለውጥን የምናይበት ወቅት ላይ ደርሰናል።

          ይህ ሊሆን ግድ ነው። ጽዋ እስኪሞላ የሚጨመርለትን ሁሉ ይሸከም እና ከሞላ በኋላ መፍሰሱ ሳይንሳዊም፤ ተፈጥሯዊም ህግ ነውና ከአቅሙ በላይ ሲሞላሁሉም ነገር ይፈስሳል። ከየአቅጣጫው ሕዝቡን ገፍተው እዚህ አደረሱት። እነሆም የሕዝብን የቁጣ ወላፈን ትላንት በኦሮሞ ወንድሞቻችን፣ ዛሬ ደግሞ በጎንደር አዩት።ነገ በደቡብ፣ ከዚያም በምስራቅ እና በምእራብ ይቀጥላል። ይህ ቁጣ የመጀመርያው እንጂ የመጨረሻው አይደለም።

          “የዚህን መንግስት ያህል በህዝብ ክፉኛ የተጠላ ስርዓት በህይወት ዘመኔ አይቼም ሆነ ሰምቼ አላየሁም።” ሲሉ አንድ ከፍተኛ የኢህአኤግ ባለስልጣን ሲናገሩአድምጫለሁ። ከውስጣዊ ሰዎች  እንደምንሰማው ከሆነ 90 በመቶ የሚሆኑት የኦህዴድ እና የብአዴን አመራር አባላት ከህወሃት ጋር ሆድና ጀርባ ከሆኑ ሰንበትበት ብለዋል፤ የህዝቡ በደል አንገሽግሿቸው ህዝባዊውን አመጽ ለመቀላቀል በመጠባበቅ ላይ ናቸው።  በራሱ በአገዛዙ ውስጥ ያሉ ሁለተኛ ረድፈኞችሳይቀሩ እንደሚመሰክሩት፤ የህወሃት ወንጀል ደርግ ከሰራው ወንጀል እንኳን ሊወዳደር አይችልም። የበደሉን ብዛት እና የዝርፊያውን ግዙፍነት የሚመሰክሩት ሁሉ ይህስርዓት በቅርጽ እንጂ በይዘት እንደሌለ ነው እየመሰከሩ ያሉት። “በአሁን ሰዓት በመንግስት ስም የሚነግድ የማፍያ ቡድን እንጂ መንግስት የለም!” ነው ያለው አንድ ከፍተኛ የብአዴን ሰው።

         ሕዝቡ ይህንን ሰርዓት ለምን አይጥላው? ሁሉም ስለታፈነ ሕዝብ ነው የሚናገሩት።  አንድ ለአምስት ተጠረንፎ የተያዘ ሕዝብ፣ እስከውስጥ ገመናውበኢህአዲግኛ መስፈርት እየተገመገመ የሚሰቃይ ሕዝብ፣ ሌት ተቀን በሙስና እንደመዥገር እየተበዘበዘ ያለ ሕዝብ። ኢትዮጵያ የሚለውን ቃል እንኳን ለመጥራትእየተጸየፉ፣ ሀገርን እና ታሪካዊ ባንድራዋን እየጠሉ፣ … እንዴት ሊቆዩ ይችላሉ?

          ለችግሮች ሁሉ መፍትሄያቸው ጠመንጃ ነው። የጎንደሩንም ችግር በጠመንጃ ለመፍታት እየመከሩ ይገኛሉ። በመጀመርያ ከህዝቡ መሳርያ መንጠቅ። ከዚያም እንደ በኦሮሞ ወጣቶች እንዳደረግነው በአልሞ ተኳሾች አማጺውን መልቀም ይኖርብናል ሲሉ ዶ/ር ደብረጽዮን መናገራቸው እየተሰማ ነው። ከ500 ያላነሱ የኦሮሞ ወገኖቻችንን ጨርሰው ሲያበቁ፤ እርምጃው ተመጣጣኝ እና ፍትሃዊ ነው ሲሉ ቀለዱብን። ለመሆኑ ከአንድ ሰብዓዊ ፍጡር እንደዚህ አይነት ፍጹምአረመኔያዊ ነገር ይሰማል?  የጭካኔ ጣርያው የት ድረስ ነው?…

መገናኛ ብዙሃን ላይ እየወጡ በህዝብ ላይ የሚያላግጡት ነገር ደግሞ እጅግ ያሳምማል።  ለጥያቄዎች ሁሉ አንድ መልስ ነው ያላቸው። መልሱም “ሻዕቢያ”የሚባል ግዑዝ ነገር። የኦሮሞ ሕዝብ ሰቆቃ ይቁም ብለው የተነሱት ወጣቶች በሙሉ “የታጠቁ እና የተደራጁ የሻዕቢያ ቡድኖች ናቸው” ተባልን። የወልቃይት የማንነትጥያቄ ያነሱት ወገኖች ሁሉ ያሻዕቢያ ተላላኪዎች እንደሆኑ ነገሩን። የታገልነው ለነጻነታችን እንጂ ትግሬ ለመሆን አይደለም ያሉት ከራሳቸው ውስጥ ያሉ ታጋዮችምየሻዕቢያ መልዕክተኞች ናቸው።  የችግሮቻቸው ሁሉ መንስኤው ሻእቢያ ነው። ይህ ሊሆን ይችላል። 10 ሰው የሻዕቢያ ተላላኪ ሊሆን ይችላል። 100 ሰውም የሻዕቢያ ተላላኪ ሊሆን ይችላል። 1000 ሰው የሻዕቢያ ተላላኪ ሊሆን ይችላል። አንድ ሚልየን ህዝብ የሻዕቢያ ተላላኪ ከሆነ ግን ከነጻነት ትግሉ ጀርባ ሻዕቢያ እንዳለ ነው እየነገሩን ያሉት።           ፖለቲካን እንደ ማስንቆ እየቃኘ የሚጫወትበትን ህዝብ፣ እነሱ የሚናገሩትን ሁሉ እንደ ስንዴ እየፈለፈለ እንደሚያበጥረው እንኳን አይገነዘቡም። 

       የምስራቁ ፈላስፋ ኮንፋሽየስ “ትልቁ እውቀት የራስን የድንቁርና መጠን ጠንቅቆ ማወቅ ነው“ ይለናል። ይህንን ሁሉ ህዝብ የሻዕቢያ ተላላኪ ሲሉ በድፍረትመናገራቸው የድንቁርናቸው መጠን ምን ያህል የወረደ መሆኑን ያመላክተናል።  “በወልቃይት ጠገዴ ስቃይ እና እስር ይብቃ!“ የሚለው መፈክር የሻዕቢያ ከሆነ ሻዕቢያለወልቃይት ህዝብ መብት በመነሳቱ ሊወገዝ ሳይሆን ይልቁንም ሊወደስ ይገባዋል። እንደ ጣዕረ-ሞት እየተከተለ እንቅልፍ የሚነሳቸው ሻዕቢያ “ለሱዳን የተሸጠውድንበራችን ባስቸኳይ ይመለስ!“ የሚል መልዕክት ይዞ ህዝብን ማሰለፍ ከቻለ ወዳጅ እንጂ ጠላት አይሆንም።

        ሁሌም ህዝብን ማታለል የሚችሉ ይመስላቸዋል። ትላንት የተጫወቱበትን ካርታ ሳይቀይሩ ዛሬም ለመጫወት ይሞክራሉ። በኮብልስቶን፣ በአንሰተኛና ጥቃቅን…ወዘተ የተያዘ ወጣት ሁሉ ፣ በደል ያላመረረው፣ ንቀት ያላስቆጣው መሆኑን አሁን ማረጋገጥ ይችላሉ። 

ካሁን በኋላ እነሱ ሊያደርጉ የሚችሉት አንድ አስፈሪ ነገር ቢኖር፤  የትግራይን ህዝብ ከወንድሙ የአማራና ከኦሮሞ ህዝብ ጋር ደም ማቃባት ብቻ ነው። እዚህ ላይ ነው ከፍተኛ ጥንቃቄ መደረግ የሚገባው። የትግራይ ህዝብ የዚህ አናሳ ቡድን እዳ ከፋይ መሆን የለበትም።  የትግራይ ሕዝብም በቡድን-በቡድን ተከፋፍሎ የሚሰቃይ መሆኑን መረዳት ይኖርብናል። የተገመገመ፣ የሚገመገም እና ለት ተቀን የሚገመግም ቡድን!  ይህ ሕዝብም ነጻ መውጣት አለበት።

“የጎንደር ሕዝባዊ ትግል ኢትዮጵያን የማዳን ትግል ነው!!”– (ሸንጎ)

$
0
0

የኢትዮጵያ ሕዝብ የጋራ ትግል ሸንጎ (ሸንጎ)

Ethiopian People’s Congress for United Struggle (Shengo)

www.ethioshengo.org     shengo.derbiaber@gmail.com

ሐምሌ 25 ቀን 2008 ዓ. ም    August 1, 2016

shengoሰሞኑን በጎንደር ከተማና አካባቢው የፈነዳው ሕዝባዊ እምቢባይነት ታፍኖ ሲብላላ የቆየው የሕዝብ እንቅስቃሴ ክምችት ውጤት ነው።ይህ ሰሞኑን የተቀሰቀሰው ሕዝባዊ ትግል ላለፉት አርባ ዓመታት በተለይም ላለፉት 25ዓመታት ሕወሃት የተባለው አገር አጥፊ ድርጅት አገሪቱን ሸንሽኖ፣ዳርድንበሯን ቆራርሶ ለባእዳን በመስጠትና በመቸርቸር፣ ሕዝቡን በጎጥ ጎራ አሰልፎ እንዲተላለቅና በግርግር የትግራይን ነጻነትና “ትልቋን ትግራይን” ለመመስረት የተነሳበትን ዓላማ  እውን ለማድረግ ከቋጠረው ሴራ የተወለደ ሕዝባዊ ተቃውሞና እምቢ ባይነት ነው። ዓላማውን ለማሳካትና ትግራይን በራሷ እንድትቆም በሚል ቀቢጸ ተስፋ የአጎራባች የኢትዮጵያ ክፍለሃገር ለም መሬቶችንና ሕዝቡን በሃይል አስገድዶ የትግራይን  መሬት ከሚገባው በላይ ለጥጦ ሲከልል፣ ለተነሳበት  ዓላማ መሳካት አያሌ ተንኮሎችን ሲሸርብና ሲዘጋጅ የጎንደር ሕዝብ በዝምታ አላየውም። የነበረውን ተንኮል ገና ከጅምሩ ለማክሸፍ ያደረገው ትግልና የከፈለው መስዋእትነት ብዙ ነው፤አሁን በዚህ ደረጃ ላይ ደርሶ የአገራችንን ሕዝብ ከዳር እስከዳር ያስቆጣና ያነሳሳ  ሕዝባዊ እምቢባይነት የዚያ ጥርቅም ውጤት ነው።ይህ በተለያዩ ያገሪቱ ክፍሎች የተካሄደውና በመካሄድ ላይ ያለው ሕዝባዊ ትግል በደሃውና አገሩን በሚወደው የትግራይ ሕዝብ ላይ ያነጣጠረ የጥቃት እርምጃ ሳይሆን እራሱን የትግራይን ሕዝብ ቀፍድደው በስሙ ከሚነግዱና ለእልቂት ከሚጋብዙት ባንዳ ተወላጆቹ ቁጥጥር ነጻ ለማውጣት እንደሆነ መታወቅ አለበት።የትግራይ ተወላጅ የሆኑት የኢትዮጵያ ንጉሠነገሥት አጼ ዩሃንስ አንገታቸውን የሰጡበትና የጦር መሪው ራስ አሉላ አባነጋ እንዲሁም አያሌ የትግራይ ተወላጆች በከፈሉት መስዋዕትነት ተከብሮ የቆየውን የኢትዮጵያ አገራችንን  ዳር ድንበር በዛው በትግራይ መሬት የበቀሉ አገር አጥፊና ከሃዲ ስብስቦች ኤርትራን ለጣልያን ቡችሎች፣የጉሙዝና የቤኒሻንጉልን አዋሳኝ ሰፊ ለም መሬት ለሱዳኖች(ለደርቡሾች) አሳልፈው ሲሰጡ ማየት እንኳንስ ለትግራይ ተወላጅ ቀርቶ ለአፍሪካ ነጻነትና ለኢትዮጵያ አንድነት የሚቆረቆር አፍሪካዊውን ልብ ያደማል፣ስሜት ይቀሰቅሳል። በስሙ ሥልጣን ላይ የተቀመጡት ከይሲዎች የትግራይ ተወላጅ አሁን በአገሪቱ በተለያዩ ቦታዎች የሚካሄድ ሕዝባዊ ትግል እንዳይቀላቀል፣ፈርቶ እንዲሸሽና በጠላትነት ፈርጆ ለመከላከል ጦር እንዲመዝ  ያላሰለሰ ቅስቀሳና ጥሪ ፣ብሎም በታጋዩ ሕዝብ ስም የሚያስፈራሩ መልእክቶችን በብዙሃን መገናኛዎች፣ማለትም በፌስቡክ፣በቫይበርና በመሳሰሉት መርዛቸውን እየረጩ ስለሆነ ከወጥመዱ ውስጥ እንዳይገባ፣ከትግሉ ጎራ እንዳያፈገፍግየኢትዮጵያ ሕዝብ የጋራ ትግል ሸንጎ ያሳስባል።በተመሳሳይም ደረጃ የኢትዮጵያን አንድነትና ሰላም፣የሕዝቡን ግንኙነትና አብሮ መኖር የማይፈልጉ፣በግርግር ሊጠቀሙ የሚሹ የውስጥና የውጭ አገር ጠላቶች ይህን ሕዝባዊና ሰላማዊ ትግል በመጥለፍ ወደሌላ አቅጣጫ ለመለወጥና ትርምስ እንዲፈጠር የተለያየ ዘዴ መጠቀማቸው ስለማይቀር ሰለባ ላለመሆን ነቅቶ መጠበቅ እንደሚያሻ ሸንጎ ያስገነዝባል። በተጨማሪም በሰላምና እርቅ ስም የተወሰኑ ስብስቦችን ብቻ ያካተተ፣ሌሎቹን አገር ወዳዶች ያገለለ በውጭ ሃይሎች ምርጫና ግፊት  የጨቋኞችና የዘራፊዎች ስርዓት ዳግም እንዳይንሰራራ ነቅቶ መጠበቅ እንደሚያስፈልግ  ሸንጎ ያሳስባል።የጉዳዩ ባለቤት የሆነው የኢትዮጵያ ሕዝብ እንጂ የውጭ ሃይሎች ስላልሆኑ መድረኩንና ውሳኔውን እንዳይቀሙት መከላከል ተገቢ ነው።

13681020_626757367488618_5689809962206469958_n

ይህን ሕዝባዊ ትግል ከዳር ለማድረስና ግቡን እንዲመታ በተለያዩ ቦታዎች የሚካሄደው ትግል መቀናጀት ይኖርበታል።ለዚህ በአገር ውስጥ የሚገኙት የፖለቲካ ድርጅቶች ከፍርሃትና እርስ በርስ ከመናቆር ድባብ ወጥተው እጅ ለእጅ ተያይዘውና ግንባር ፈጥረው አመራር ሊሰጡት ይገባል።የሕዝቡ ትግል በአንድ ቦታ ላይ ብቻ አተኩሮ ለአገዛዙ መቺ ሃይል አመቺ እንዳይሆንና ትግሉ በሃይል እንዳይዳፈን በተለያዩ ያገሪቱ ክፍሎች መቀጣጠል፣ አገር አቀፍ መሆን ይኖርበታል።

ገዢው ቡድን ጊዜ ለመግዛትና ለማዘናጋት ድርድር ልቅረብ ቢል ካለምንም ቅድመ ሁኔታ መቀበል ለጥፋት እጅን መስጠት ከመሆኑም በላይ ህልውናውን ማወቅ ነው።ስለሆነም ፖለቲካ እስረኞች ሳይፈቱ፣የመጻፍና የመሰብሰብ መብት ሳይረጋገጥ፣ለሽግግር መንግሥት ምስረታ የሚያበቃ ውል ሳይፈረም፣ለቁጥጥርና ለጭቆና የሚውሉ ሕጎች መሰረዛቸው ሳይረጋገጥ፣ በይሆናል ተስፋ ትግሉን ማብረድና አደባባይ የወጣው ተመልሶ እቤቱ እንዲገባ ማድረግ ለቀጣዩ አደጋና ጥቃት እራስን አጋልጦ መስጠት ይሆናል።ስለሆነም ከእራሳችን ተመክሮ ከ97ቱ ተለምዶ መማር የግድ ይላል።መሪና በቂ ዝግጅት የሌለው የሕዝብ ሰላማዊ ትግል ቀርቶ ታንክና መድፍ፣አይሮፕላንና መሳሪያ ያነገተ አያሌ ወታደር አሰልፎ ባልተቀናጀ አመራር ተዝረክርኮ የተካሄደው መፈንቅለ መንግሥት ሳይሳካ ቡጢ በጨበጠ የመንግሥት ደጋፊ ወገን መረታቱን ከቅርቡ የቱርክ ሁኔታ መረዳት እንችላለን። ይህን ስንጠቅስ የቱርክን መፈንቅለ መንግሥት በመደገፍ ሳይሆን ያልተደራጀና አመራር የሌለው ተቃውሞና ትግል ግቡን እንደማይመታ ለማሳየት ነው።

አሁን ሕዝብ ከመንግሥት ነኝ ባይ አገር አጥፊ ቡድን ጋር ደም ተቃብቷል፤ሕዝብና አገዛዙ ሆድና ጀርባ ሆኗል፤በባለሥልጣኖቹ መካከል ድንጋጤ የፈጠረው ውዝግብና ትርምስ እየጎላ መጥቷል፡፤ትናንትና ሽንጣቸውን ገትረው ይከራከሩለት የነበሩት ባለሥልጣኖች ዛሬ አደባባይ ወጥተው ስርዓቱን በመኮነን ላይ ናቸው።ሌሎቹም ወደውጭ አገር ንብረትና ቤተሰባቸውን በማሸሽ ላይ ናቸው።ይህ ሁሉ ስርዓቱ መዳከሙን ያሳያል።አሁን ሕዝብና አገዛዙ(ስርዓቱ) ከማይታረቅ ቅራኔ ውስጥ ገብቷል።ጠግኖ መቀጠል አይቻልም። እርቅና ሰላም የሚወርደው ይህ እኩይ መንግሥት ከስልጣን ሲወርድ ብቻ ነው።ከስልጣን መውረዱም ብቻ ሳይሆን ሕዝቡን የሚወክል፣በሕግ የበላይነት የሚያምን፣የአገሪቱን የግዛት አንድነት በሚያረጋግጥ፣የዜጎችን እኩልነትና መብት የሚያከብርና የሚያስከብር የሽግግር ብሎም ቋሚ መንግሥት ሲተካ ብቻ ነው። በግርግር የታጠቀ ወይም በውጭ ሃይሎች የሚረዳና ለውጭ ሃይሎች ጥቅም የቆመ ሃይል የሕዝቡን ድል ነጥቆ እንዳይወስድና ተመሳሳይ የመከራ አገዛዝ እንዳይሰፍን ነቅቶ መጠበቅ ያስፈልጋል።ከግብጽና ከሌሎቹም የሕዝብ ትግል ተነስቶ ከከሰመባቸው አገሮች የቅርብ ጊዜ ልምድ መማር ይጠቅማል።

የኢትዮጵያ ሕዝብ የጋራ ትግል ሸንጎ ይህ ሕዝባዊ ትግል የተሳካ እንዲሆን፣በአመራር በኩል ያለውን ክፍተት ለመሙላት ከሌሎቹ አገር ወዳድ ሃይሎች፣ የማህበረሰብ ተቋማትና የፖለቲካ ድርጅቶች ጋር በመተባበር የሚቻለውን ሁሉ ለማድረግ ቃል ይገባል፤አመሰራረቱም ለዚያው ዓላማ ነው።አሁንም በአገር ቤት ካሉት የፖለቲካ ድርጅቶች ጋር የቅርብ ግንኙነት አድርጎ ትግሉን በድፍረት እንዲመሩት የተቻለውን በማድረግ ላይ ይገኛል።

የኢትዮጵያ አገራችን የወደፊት ዕድልና የሕዝቡ ሁኔታ ሸንጎን  እጅግ ያሳስበዋል፣ያስጨንቀዋልም።ለአገርና ለወገን የምታስቡ የፖለቲካ ድርጅቶች፣የሲቪክ ማህበራት፣የማህበረሰብ ስብስቦች ሁሉ፣በየምክንያቱ ተነጣጥለን የምናካሂደው ትግል ዋጋ ቢስና ጊዜው ያለፈበት መሆኑን አውቀን ከሕዝቡ ጎን ቆመን ትግሉን መሳተፍ እንደሚኖርብን ማወቅ ይገባናል።እንደተለመደው እንቀጥላለን ማለት የገዢውን መደብ ዕድሜ ማርዘም ነው። እንዳለፈው ጊዜ  ለትብብር የሚደረገውን ጥሪ ጆሮ ዳባ ልበስ ብሎ በየፊናው መባከን አሁን መስዋዕትነት እየከፈለ ያለውን ሕዝብ አውራ የሌለው መንጋ አድርጎ ለበለጠ አደጋ ማጋለጥ መሆኑን ልንረዳው ይገባል።

የሃይማኖት መሪዎችም በአገራችሁና በወገናችሁ ላይ የሚደርሰውን ግፍና በደል አውግዙ።እንደ ኢየሱስ ክርስቶስና ነብዩ ሞሃመድ ለሰው ልጆች ነጻነትና እኩልነት፣ክብር፣ለፈሪሃ እግዚአብሔር ታገሉ።ለአገር አንድነትና ነጻነትም እንደአቡነ ጴጥሮስና እንደ ደጃዝማች ዑመር ሰመተር፣እንደ ቢትወደድ አሊሚራህ እምቢ በሉ።ታቦት ተሸክመው በጦር ሜዳ ተሰልፈው ያገሪቱን ነጻነት እንዳስከበሩት የትናንቱ አባቶች እናንተም ያገራችሁን አንድነት ዛሬ አስከብሩ።የራቀውን ምዕመናን በስነምግባራችሁ፣በአገርና ሕዝብ ወዳድነታችሁ አሳምናችሁ ሳቡት።ለአገርና ለሕዝብ ጥቅም መታገልና መቆም ማለት አምላክን መራቅና መካድ አይደለም።አምላክን መካድ ማለት ክፉ ከሚሰሩት ጋር መወገን፣ግድያን፣ዘረፋንና፣ጭቆናን እያዩ በዝምታ መቀበል ነው።

የኢትዮጵያ መለዮ ለባሽም ወልዶና አሳድጎ ለዚህ ሙያ ያበቃህ ደሃ ሕዝብ መብቱ ሲገፈፍና ሲጨቆን ፣በአምባገነኖች ሲረገጥ መሣሪያ ሆነህ አታገልግል።ደመወዝህ ፣ስንቅና ትጥቅህ ከደሃው  ሕዝብ ጉሮሮ እየተነጠቀ ከሚሰበሰብ ግብር ነውና በራስህ ላይ አትዝመትበት፣በጉሮርህ ላይም አጥንት አትቀርቅርበት።ገዢው ቡድን በመለዮ ከፋፍሎ ሊያጫርስህ፣የአገርህን አንድነት አፍርሶ ሙያ ቢስ ሊያደርግህ ታጥቆ የተነሳ መሆኑን ተገንዝበህ ከወገንህ፣ከአባትህ፣ከእናትህ፣ከወንድምና ከእህትህ ጎን ተሰልፈህ የጋራ መብትህን አስከብር።በወገኖችህ ደም መታጠብ ይብቃህ።በገዳይነት ከምትወነጀል ይልቅ በአገር አዳኝነት መመስገኑ እንደሚጠቅምህና እንደሚያኮራህ እወቅ።

የኢትዮጵያ ሕዝብ የጋራ ትግል ሸንጎ(ሸንጎ)በትግል መስኩ ላይ ወጥቶ ድምጹን ከሚያሰማውና ደሙን ከሚያፈሰው፣የአማራ፣ የኦሮሞ፣የኦጋዴን፣የቤንሻንጉል፣የትግራይ፣የጋምቤላ፣የአፋር ማህበረሰብ ጋር መቆሙንና፣በአገር ውስጥና ውጭ አገር በሚችለው መንገድ ድጋፍና ተሳትፎ እንደሚያደርግ ሊያረጋግጥ ይወዳል።

ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ

 

 

 


የጎንደር ሕዝባዊ ትግል ኢትዮጵያን የማዳን ትግል ነው!! –የኢትዮጵያ ሕዝብ የጋራ ትግል ሸንጎ (ሸንጎ)

$
0
0

ሐምሌ 25 ቀን 2008 ዓ. ም    August 1, 2016

shengoሰሞኑን በጎንደር ከተማና አካባቢው የፈነዳው ሕዝባዊ እምቢባይነት ታፍኖ ሲብላላ የቆየው የሕዝብ እንቅስቃሴ ክምችት ውጤት ነው።ይህ ሰሞኑን የተቀሰቀሰው ሕዝባዊ ትግል ላለፉት አርባ ዓመታት በተለይም ላለፉት 25ዓመታት ሕወሃት የተባለው አገር አጥፊ ድርጅት አገሪቱን ሸንሽኖ፣ዳርድንበሯን ቆራርሶ ለባእዳን በመስጠትና በመቸርቸር፣ ሕዝቡን በጎጥ ጎራ አሰልፎ እንዲተላለቅና በግርግር የትግራይን ነጻነትና “ትልቋን ትግራይን” ለመመስረት የተነሳበትን ዓላማ  እውን ለማድረግ ከቋጠረው ሴራ የተወለደ ሕዝባዊ ተቃውሞና እምቢ ባይነት ነው። ዓላማውን ለማሳካትና ትግራይን በራሷ እንድትቆም በሚል ቀቢጸ ተስፋ የአጎራባች የኢትዮጵያ ክፍለሃገር ለም መሬቶችንና ሕዝቡን በሃይል አስገድዶ የትግራይን  መሬት ከሚገባው በላይ ለጥጦ ሲከልል፣ ለተነሳበት  ዓላማ መሳካት አያሌ ተንኮሎችን ሲሸርብና ሲዘጋጅ የጎንደር ሕዝብ በዝምታ አላየውም። የነበረውን ተንኮል ገና ከጅምሩ ለማክሸፍ ያደረገው ትግልና የከፈለው መስዋእትነት ብዙ ነው፤አሁን በዚህ ደረጃ ላይ ደርሶ የአገራችንን ሕዝብ ከዳር እስከዳር ያስቆጣና ያነሳሳ  ሕዝባዊ እምቢባይነት የዚያ ጥርቅም ውጤት ነው።ይህ በተለያዩ ያገሪቱ ክፍሎች የተካሄደውና በመካሄድ ላይ ያለው ሕዝባዊ ትግል በደሃውና አገሩን በሚወደው የትግራይ ሕዝብ ላይ ያነጣጠረ የጥቃት እርምጃ ሳይሆን እራሱን የትግራይን ሕዝብ ቀፍድደው በስሙ ከሚነግዱና ለእልቂት ከሚጋብዙት ባንዳ ተወላጆቹ ቁጥጥር ነጻ ለማውጣት እንደሆነ መታወቅ አለበት።የትግራይ ተወላጅ የሆኑት የኢትዮጵያ ንጉሠነገሥት አጼ ዩሃንስ አንገታቸውን የሰጡበትና የጦር መሪው ራስ አሉላ አባነጋ እንዲሁም አያሌ የትግራይ ተወላጆች በከፈሉት መስዋዕትነት ተከብሮ የቆየውን የኢትዮጵያ አገራችንን  ዳር ድንበር በዛው በትግራይ መሬት የበቀሉ አገር አጥፊና ከሃዲ ስብስቦች ኤርትራን ለጣልያን ቡችሎች፣የጉሙዝና የቤኒሻንጉልን አዋሳኝ ሰፊ ለም መሬት ለሱዳኖች(ለደርቡሾች) አሳልፈው ሲሰጡ ማየት እንኳንስ ለትግራይ ተወላጅ ቀርቶ ለአፍሪካ ነጻነትና ለኢትዮጵያ አንድነት የሚቆረቆር አፍሪካዊውን ልብ ያደማል፣ስሜት ይቀሰቅሳል። በስሙ ሥልጣን ላይ የተቀመጡት ከይሲዎች የትግራይ ተወላጅ አሁን በአገሪቱ በተለያዩ ቦታዎች የሚካሄድ ሕዝባዊ ትግል እንዳይቀላቀል፣ፈርቶ እንዲሸሽና በጠላትነት ፈርጆ ለመከላከል ጦር እንዲመዝ  ያላሰለሰ ቅስቀሳና ጥሪ ፣ብሎም በታጋዩ ሕዝብ ስም የሚያስፈራሩ መልእክቶችን በብዙሃን መገናኛዎች፣ማለትም በፌስቡክ፣በቫይበርና በመሳሰሉት መርዛቸውን እየረጩ ስለሆነ ከወጥመዱ ውስጥ እንዳይገባ፣ከትግሉ ጎራ እንዳያፈገፍግየኢትዮጵያ ሕዝብ የጋራ ትግል ሸንጎ ያሳስባል።በተመሳሳይም ደረጃ የኢትዮጵያን አንድነትና ሰላም፣የሕዝቡን ግንኙነትና አብሮ መኖር የማይፈልጉ፣በግርግር ሊጠቀሙ የሚሹ የውስጥና የውጭ አገር ጠላቶች ይህን ሕዝባዊና ሰላማዊ ትግል በመጥለፍ ወደሌላ አቅጣጫ ለመለወጥና ትርምስ እንዲፈጠር የተለያየ ዘዴ መጠቀማቸው ስለማይቀር ሰለባ ላለመሆን ነቅቶ መጠበቅ እንደሚያሻ ሸንጎ ያስገነዝባል። በተጨማሪም በሰላምና እርቅ ስም የተወሰኑ ስብስቦችን ብቻ ያካተተ፣ሌሎቹን አገር ወዳዶች ያገለለ በውጭ ሃይሎች ምርጫና ግፊት  የጨቋኞችና የዘራፊዎች ስርዓት ዳግም እንዳይንሰራራ ነቅቶ መጠበቅ እንደሚያስፈልግ  ሸንጎ ያሳስባል።የጉዳዩ ባለቤት የሆነው የኢትዮጵያ ሕዝብ እንጂ የውጭ ሃይሎች ስላልሆኑ መድረኩንና ውሳኔውን እንዳይቀሙት መከላከል ተገቢ ነው።

ይህን ሕዝባዊ ትግል ከዳር ለማድረስና ግቡን እንዲመታ በተለያዩ ቦታዎች የሚካሄደው ትግል መቀናጀት ይኖርበታል።ለዚህ በአገር ውስጥ የሚገኙት የፖለቲካ ድርጅቶች ከፍርሃትና እርስ በርስ ከመናቆር ድባብ ወጥተው እጅ ለእጅ ተያይዘውና ግንባር ፈጥረው አመራር ሊሰጡት ይገባል።የሕዝቡ ትግል በአንድ ቦታ ላይ ብቻ አተኩሮ ለአገዛዙ መቺ ሃይል አመቺ እንዳይሆንና ትግሉ በሃይል እንዳይዳፈን በተለያዩ ያገሪቱ ክፍሎች መቀጣጠል፣ አገር አቀፍ መሆን ይኖርበታል።

ገዢው ቡድን ጊዜ ለመግዛትና ለማዘናጋት ድርድር ልቅረብ ቢል ካለምንም ቅድመ ሁኔታ መቀበል ለጥፋት እጅን መስጠት ከመሆኑም በላይ ህልውናውን ማወቅ ነው።ስለሆነም ፖለቲካ እስረኞች ሳይፈቱ፣የመጻፍና የመሰብሰብ መብት ሳይረጋገጥ፣ለሽግግር መንግሥት ምስረታ የሚያበቃ ውል ሳይፈረም፣ለቁጥጥርና ለጭቆና የሚውሉ ሕጎች መሰረዛቸው ሳይረጋገጥ፣ በይሆናል ተስፋ ትግሉን ማብረድና አደባባይ የወጣው ተመልሶ እቤቱ እንዲገባ ማድረግ ለቀጣዩ አደጋና ጥቃት እራስን አጋልጦ መስጠት ይሆናል።ስለሆነም ከእራሳችን ተመክሮ ከ97ቱ ተለምዶ መማር የግድ ይላል።መሪና በቂ ዝግጅት የሌለው የሕዝብ ሰላማዊ ትግል ቀርቶ ታንክና መድፍ፣አይሮፕላንና መሳሪያ ያነገተ አያሌ ወታደር አሰልፎ ባልተቀናጀ አመራር ተዝረክርኮ የተካሄደው መፈንቅለ መንግሥት ሳይሳካ ቡጢ በጨበጠ የመንግሥት ደጋፊ ወገን መረታቱን ከቅርቡ የቱርክ ሁኔታ መረዳት እንችላለን። ይህን ስንጠቅስ የቱርክን መፈንቅለ መንግሥት በመደገፍ ሳይሆን ያልተደራጀና አመራር የሌለው ተቃውሞና ትግል ግቡን እንደማይመታ ለማሳየት ነው።

አሁን ሕዝብ ከመንግሥት ነኝ ባይ አገር አጥፊ ቡድን ጋር ደም ተቃብቷል፤ሕዝብና አገዛዙ ሆድና ጀርባ ሆኗል፤በባለሥልጣኖቹ መካከል ድንጋጤ የፈጠረው ውዝግብና ትርምስ እየጎላ መጥቷል፡፤ትናንትና ሽንጣቸውን ገትረው ይከራከሩለት የነበሩት ባለሥልጣኖች ዛሬ አደባባይ ወጥተው ስርዓቱን በመኮነን ላይ ናቸው።ሌሎቹም ወደውጭ አገር ንብረትና ቤተሰባቸውን በማሸሽ ላይ ናቸው።ይህ ሁሉ ስርዓቱ መዳከሙን ያሳያል።አሁን ሕዝብና አገዛዙ(ስርዓቱ) ከማይታረቅ ቅራኔ ውስጥ ገብቷል።ጠግኖ መቀጠል አይቻልም። እርቅና ሰላም የሚወርደው ይህ እኩይ መንግሥት ከስልጣን ሲወርድ ብቻ ነው።ከስልጣን መውረዱም ብቻ ሳይሆን ሕዝቡን የሚወክል፣በሕግ የበላይነት የሚያምን፣የአገሪቱን የግዛት አንድነት በሚያረጋግጥ፣የዜጎችን እኩልነትና መብት የሚያከብርና የሚያስከብር የሽግግር ብሎም ቋሚ መንግሥት ሲተካ ብቻ ነው። በግርግር የታጠቀ ወይም በውጭ ሃይሎች የሚረዳና ለውጭ ሃይሎች ጥቅም የቆመ ሃይል የሕዝቡን ድል ነጥቆ እንዳይወስድና ተመሳሳይ የመከራ አገዛዝ እንዳይሰፍን ነቅቶ መጠበቅ ያስፈልጋል።ከግብጽና ከሌሎቹም የሕዝብ ትግል ተነስቶ ከከሰመባቸው አገሮች የቅርብ ጊዜ ልምድ መማር ይጠቅማል።

የኢትዮጵያ ሕዝብ የጋራ ትግል ሸንጎ ይህ ሕዝባዊ ትግል የተሳካ እንዲሆን፣በአመራር በኩል ያለውን ክፍተት ለመሙላት ከሌሎቹ አገር ወዳድ ሃይሎች፣ የማህበረሰብ ተቋማትና የፖለቲካ ድርጅቶች ጋር በመተባበር የሚቻለውን ሁሉ ለማድረግ ቃል ይገባል፤አመሰራረቱም ለዚያው ዓላማ ነው።አሁንም በአገር ቤት ካሉት የፖለቲካ ድርጅቶች ጋር የቅርብ ግንኙነት አድርጎ ትግሉን በድፍረት እንዲመሩት የተቻለውን በማድረግ ላይ ይገኛል።

የኢትዮጵያ አገራችን የወደፊት ዕድልና የሕዝቡ ሁኔታ ሸንጎን  እጅግ ያሳስበዋል፣ያስጨንቀዋልም።ለአገርና ለወገን የምታስቡ የፖለቲካ ድርጅቶች፣የሲቪክ ማህበራት፣የማህበረሰብ ስብስቦች ሁሉ፣በየምክንያቱ ተነጣጥለን የምናካሂደው ትግል ዋጋ ቢስና ጊዜው ያለፈበት መሆኑን አውቀን ከሕዝቡ ጎን ቆመን ትግሉን መሳተፍ እንደሚኖርብን ማወቅ ይገባናል።እንደተለመደው እንቀጥላለን ማለት የገዢውን መደብ ዕድሜ ማርዘም ነው። እንዳለፈው ጊዜ  ለትብብር የሚደረገውን ጥሪ ጆሮ ዳባ ልበስ ብሎ በየፊናው መባከን አሁን መስዋዕትነት እየከፈለ ያለውን ሕዝብ አውራ የሌለው መንጋ አድርጎ ለበለጠ አደጋ ማጋለጥ መሆኑን ልንረዳው ይገባል።

የሃይማኖት መሪዎችም በአገራችሁና በወገናችሁ ላይ የሚደርሰውን ግፍና በደል አውግዙ።እንደ ኢየሱስ ክርስቶስና ነብዩ ሞሃመድ ለሰው ልጆች ነጻነትና እኩልነት፣ክብር፣ለፈሪሃ እግዚአብሔር ታገሉ።ለአገር አንድነትና ነጻነትም እንደአቡነ ጴጥሮስና እንደ ደጃዝማች ዑመር ሰመተር፣እንደ ቢትወደድ አሊሚራህ እምቢ በሉ።ታቦት ተሸክመው በጦር ሜዳ ተሰልፈው ያገሪቱን ነጻነት እንዳስከበሩት የትናንቱ አባቶች እናንተም ያገራችሁን አንድነት ዛሬ አስከብሩ።የራቀውን ምዕመናን በስነምግባራችሁ፣በአገርና ሕዝብ ወዳድነታችሁ አሳምናችሁ ሳቡት።ለአገርና ለሕዝብ ጥቅም መታገልና መቆም ማለት አምላክን መራቅና መካድ አይደለም።አምላክን መካድ ማለት ክፉ ከሚሰሩት ጋር መወገን፣ግድያን፣ዘረፋንና፣ጭቆናን እያዩ በዝምታ መቀበል ነው።

የኢትዮጵያ መለዮ ለባሽም ወልዶና አሳድጎ ለዚህ ሙያ ያበቃህ ደሃ ሕዝብ መብቱ ሲገፈፍና ሲጨቆን ፣በአምባገነኖች ሲረገጥ መሣሪያ ሆነህ አታገልግል።ደመወዝህ ፣ስንቅና ትጥቅህ ከደሃው  ሕዝብ ጉሮሮ እየተነጠቀ ከሚሰበሰብ ግብር ነውና በራስህ ላይ አትዝመትበት፣በጉሮርህ ላይም አጥንት አትቀርቅርበት።ገዢው ቡድን በመለዮ ከፋፍሎ ሊያጫርስህ፣የአገርህን አንድነት አፍርሶ ሙያ ቢስ ሊያደርግህ ታጥቆ የተነሳ መሆኑን ተገንዝበህ ከወገንህ፣ከአባትህ፣ከእናትህ፣ከወንድምና ከእህትህ ጎን ተሰልፈህ የጋራ መብትህን አስከብር።በወገኖችህ ደም መታጠብ ይብቃህ።በገዳይነት ከምትወነጀል ይልቅ በአገር አዳኝነት መመስገኑ እንደሚጠቅምህና እንደሚያኮራህ እወቅ።

የኢትዮጵያ ሕዝብ የጋራ ትግል ሸንጎ(ሸንጎ)በትግል መስኩ ላይ ወጥቶ ድምጹን ከሚያሰማውና ደሙን ከሚያፈሰው፣የአማራ፣ የኦሮሞ፣የኦጋዴን፣የቤንሻንጉል፣የትግራይ፣የጋምቤላ፣የአፋር ማህበረሰብ ጋር መቆሙንና፣በአገር ውስጥና ውጭ አገር በሚችለው መንገድ ድጋፍና ተሳትፎ እንደሚያደርግ ሊያረጋግጥ ይወዳል።

ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ

Tel.: 44 7937600756 , +1 9168486790  E-mail : shengo.derbiaber@gmail.com

 

 

ታላቁ የጎንደር የተቃውሞ  ሰልፍ በቢቢሲ BBC News እይታ በዘርይሁን  ሹመቴ

$
0
0

በዘርይሁን  ሹመቴ/ ከ ጀርመን

በሐምሌ 25 2008 (01 08 2016 ) ቢቢሲ BBC NEWS “Ethiopia Protests: What’s behind the trouble in Gondar?” በሚል ርእስ የአማራና የኦሮሞ ህዝቦች በገዢው የወያኔ አገዛዝ ላይ እያሳዩ ያሉትን  ህዝባዊ  አመጸኝነት በሰፊው  ዘግቦታል።

በሐምሌ 24 2008 (31 07 2016) በጎንደር  ከተማ የተደረገው  የተቃውሞ  ሰልፍ  መነሻው  የወልቃይት የአማራ  ማንንት ጥያቄ ያደደገ  እንደሆነ ቢቢሲ  በዚሁ  ዘገባው  ቢያሰፍርም በተቃውሞ  ሰልፉ ግን  በኦሮሞ  ወንድሞችና  እህቶች ላይ  የሚደረገውንም  ግፍና  ግድያ የሚያወግዙ  መፈክሮችና  ጽሁፎች  እንደነበሩ  ቢቢሲ  እማኝነቱን  በዚሁ  ዘገባው  ሰጥቷል “When Sunday’s demonstration was organized on social media, no mention was made of other issues, but during the protest banners could be seen expressing solidarity with people from the Oromia region.”

በምስል  በተደገፈ  ማስርጃ መሰረት ገዢው የወያኔ መንግስት  በንጹሀን  የኦሮሞ  ሀዝብ  ላይ እያደረገ  ያለውን ግፍ  ግድያ  እንዲሁም  እስራት  እንዲያቆም  የአማራው  ህዝብ  ድምጹን  አጉልቶ  ሲጠይቅና ሲያወግዝ ለማየት ተችሏል  https://www.youtube.com/watch?v=jz47zbUv99s

የኢትዮጵያ  መንግስት በሰብአዊ  መብት ተከራካሪ  ድርጅቶች  ከፍተኛ  ትችት  እየደረሰበት  እንደሆነም  ቢቢሲ  በዘገባው  አካቶ አስፍሯል  “Ethiopia’s government has been criticised by rights  groups for cracking down on protests and dissident voices and using anti-terror laws to silence people.” በተጨማሪም ይህ የአማራው  ህዝብ  ተቋውሞ  በአጠቃላይ  አገሪቷ  ላይ  እየተስፋፋ  የመጣውን  የህዝብ እምቢተኛነት  እና  ህዝቡ ለገዢው  ፓርቲ  ያለውን  ጥላቻ  ያሳያል  የሚል  አንድምታ  ሊኖረው  እንደሚችል  በዚሁ  ዘገባ  ቀርቧል “For some observers, the Amhara protests appear to be part of a growing anti-government feeling, which the authorities are trying to contain.”

ምንጭ

ታላቁ የጎንደር የተቃውሞ  ሰልፍ በቢቢሲ BBC News እይታ በዘርይሁን  ሹመቴ

http://www.bbc.com/news/world-africa-36940906

https://www.youtube.com/watch?v=jz47zbUv99s

 

 

በዘርይሁን  ሹመቴ

ጀርመን

 

 

 

በመለስ ስም የተሰየመው Dreamliner 787 እና መንገድ የሳተው አየር መንገድ (ጥናታዊ ዳሰሳ)

$
0
0

ከተመሰረተ 70ኛ አመቱን ያከበረው የኢትዮጵያ አየር መንገድ በቅርቡ ካስገባቸው አስራ አምስት Dreamliner 787 አውሮፕላኖች ውስጥ በመለስ ስም የተሰየመው አውሮፕላን አዲስ አበባ ገብቷል። ከዚህ በፊት የሰሜን ተራሮች፣ የአክሱም እና ታሪካዊ የሆኑ ቦታዎች ስም የተሰጣቸው Dreamliner አውሮፕላኖች ገብተዋል። ስያሜው የአገርን ቅርስ አመላካች በመሆኑ ብዙ የሚያወዛግብ ጉዳይ አይደለም። ባለፈው ሳምንት ግን ET-ATK የሚል የመዝገብ ቁጥር (Registration Number) ያለው፤ በመለስ ዜናዊ ስም “መለስ” የሚል ስያሜ የተሰጠው  አውሮፕላን ቦሌ አለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ገብቷል።

                         አውሮፕላኑ የገባበት ሳምንት በኦሮሚያ እና በአማራ ክልልሎች ህዝባዊ ንቅናቄ የተነሳበት ሰሞን በመሆኑ፤ “ሆድ የባሰውን ህዝብ ይባስ ያነሳሳል” በሚል ስጋት በኢትዮጵያ ዜናዎች ጭምር ዘገባው እንዳይቀርብ ተደርጓል። ድርጊቱ ግን የአየር መንገዱ ከፍተኛ ባለስልጣናት ገለልተኛ ሳይሆኑ፤ የአንድ ዘር እና ፓርቲ ደጋፊ ለመሆናቸው ማረጋገጫ ሆኖ አልፏል። እነሆ ከዚህ በታች የምናነሳቸው ጉዳዮች በአየር መንገዱ ውስጥ የሚፈጸሙ የስራ ግድፈቶችን በጥቅል የሚያሳዩ ናቸው።

በመለስ ስም የተሰየመው  Dreamliner 787 እና መንገድ የሳተው አየር መንገድ (ጥናታዊ ዳሰሳ)

 

ethiopian-787-dreamliner-630-620x413

ዳዊት ከበደ ወየሳ (አትላንታ)

 

የኢትዮጵያ አየር መንገድ መለስ ዜናዊ ከመወለዱ ዘጠኝ አመት በፊት በ1946 ዓ.ም የተመሰረተ ሲሆን፤ በወቅቱ  የመጀመሪያ በረራዎቹን ወደ ካይሮ፣ ጅቡቲ እና የመን ያደርግ ነበር። በቀዳማዊ ኃይለስላሴ ጥረት እና ክትትል ተጀምሮ፤ አሁን ሰባ አመቱን ያከበረው አየር መንገድ ሰባ ያህል አለም አቀፍ በረራዎችን ለማድረግ የበቃ ነው። ወደኋላ መለስ ብለን ካስተዋልን ደግሞ… ለዚህ ካበቁት ውስጥ ደግሞ ቀዳማዊ ኃይለስላሴ በዋናነት የሚጠቀሱ ቢሆንም፤ ድርጅቱ በስማቸው አውሮፕላን ሊሰይምላቸው ቀርቶ፤ የሳቸውን ጥረት እና ድካም የሚያሳይ ማስታወሻ እንኳን አልተወላቸውም።

 

ይህ በ’ንዲህ እንዳለ ነው እንግዲህ፤ አየር መንገዱ ቦይንግ ካምፓኒ ያደሳቸውን Dreamliner 787 አውሮፕላኖች አዲስ አበባ ማስገባት የጀመረው። እኛም ይህን ምክንያት አድርገን በአየር መንገዱ ውስጥ የሚታዩትን ብልሹ አሰራሮች በወፍ በረር እንቃኝ።

 

እርግጥ ነው። መለስ ዜናዊ የህወሃት እና የኢህአዴግ ፓርቲ ሊቀመንበር ነበር። የፖለቲካ ፓርቲው አባላት መለስ ዜናዊን ከሰው በላይ ከአምላክ በታች አድርገው ያዩታል። በስሙ ልዩ ልዩ ድርጅቶችን ከፍተዋል፤ ፋውንዴሽንም አቋቁመዋል። በቀብሩ ሰሞን… “ከአቡነ አረጋዊ ያልተናነሰ ስራ ሰርቷልና በስሙ ታቦት ሊቀረጽለት ይገባል…” ማለታቸውን ሰምተን፤ አማትበን ሳንጨርስ በመለስ ስም አውሮፕላን እንዲሰየም መደረጉ አስገርሞናል። ደጋግመን እንደምንለው… ይህ የአየር መንገዱ ከፍተኛ አካል የፖለቲካ ፓርቲ ጥገኛ እየሆነ ለመምጣቱ ዋነኛው አመላካች ነው። በአሁኑ ወቅት ከዋና ሴኩሪቲ ጀምሮ እስከ ስራ አስኪያጅ ድረስ የአየር  መንገዱ ሰራተኞች የትግራይ ተወላጆች እንዲሆኑ እየተደረገ ነው።

 

ለምሳሌ የሴኩሪቲ የጥበቃ ስራውን ሙሉ ለሙሉ የሚያከናውኑት የትግራይ ተወላጆች ናቸው። በውጭ አገር ተመድበው አየር መንገዱን በመወከል የሚሰሩት ሰዎች አብዛኞቹ እነሱ ናቸው። የበረራ አስተናጋጅ ሆነው እንዲሰሩ ምልመላ የሚደረገው ትግራይ ድረስ እየተኼደ ጭምር ነው። የግራውንድ ቴክኒሺያንነት እና የበረራ ስራውን እንዲያደርጉ ቅድሚያ ተሰጥቷቸው፤ ስልጠና እየወሰዱ ያሉት የትግራይ ልጆች ናቸው። ይህ በአየር መንገዱ ውስጥ በግልጽ የሚታይ፤ ከውጭ ሆነው ለሚታዘቡ ሰዎች ደስ የማያሰኝ አካሄድ ነው።

 

ሲጀመር… የአየር መንገዱ የቦርድ ሊቀመንበር አርከበ ዕቁባይ፤ የህወሃት ፓርቲ ማዕከላዊ ኮሚቴ አባል የነበረ ነው። ሲቀጥል… የአየር መንገዱ ስራ አስኪያጅ ተወልደ ገብረማርያም የህወሃት ፓርቲ አባል ነው። ሲሰልስ… በከፍተኛ ቁልፍ ቦታዎች የተቀመጡ  የስራ ሃላፊዎች በተመሳሳይ ሁኔታ የትግራይ ህወሃት ወይም የኢህአዴግ አባላት ናቸው። የዚህ ሁሉ መነሻው ደግሞ፤ ጠባብ ብሔረተኝነት ነው።

 

ለምሳሌ ተወልደ ወልደማርያምን እንደምሳሌ እንውሰድ። ኢህአዴግ ስልጣን ከተቆናጠጠ ግዜ ጀምሮ በአየር መንገዱ ውስጥ በተለያዩ የሃላፊነት ቦታዎች ላይ እንዲሰራ እየተደረገ ስራውን ሲለማመድ ቆይቷል። አቶ ግርማ ዋቄ CEO ሆነው ሲሰሩ፤ ለአምስት አመት የስራ ኮንትራት ነው አየር መንገዱን የተቀላቀሉት። በወቅቱ ተወልደ CFO ሆኖ በመስራት የአቶ ግርማ ዋቄ ኮንትራት እስከሚያበቃ ድረስ፤ አልጋ ወራሽ ሆኖ እንዲቆይ ነው የተደረገው። አቶ ግርማ ዋቄ አየር መንገዱን ለቀው ከወጡበት ግዜ ጀምሮ ተወልደ ላልታወቁ አመታት፤ ባልታወቀ የኮንትራት ቅጥር በሃላፊነት ቦታ ላይ ሆኖ በመስራት ላይ ይገኛል።

 

ተወልደ በአየር መንገዱ ውስጥ ፈላጭ ቆራጭ መሆኑ ብቻ ሳይሆን፤ በማን አለብኝነት የሚሰራቸው ስራዎች የሚያስደነግጡ ናቸው። ለምሳሌ የዛሬ አምስት አመት ግድም MD11 የተባለ አውሮፕላን በድንገት መጣ። ስለአውሮፕላኑ ሰራተኞች ስለማያውቁ፤ “የምን አውሮፕላን ነው?” ይላሉ።

 

“በተወልደ ትእዛዝ የመጣ ነው!” ይባላል። ከዚያ በፊት ስለዚህ አውሮፕላን ማኔጅመንቱ ምንም የሚያውቀው ነገር የለም። ድንገተኛ ዱብእዳ ነው የሆነባቸው። በኋላ ላይ ለዚህ አውሮፕላን መወጣጫ እና ማሳለጫ እንዲሆን እስከ አስር ሚሊዮን ብር ድረስ ወጪ ተደርጓል። እንዲህ እንዲህ አይነቱ ብዙ ነገሮችን መጥቀስ ይቻላል።

ለምሳሌ የቦይንግ 757 ጉዳይ እንመልከት። እነዚህ አውሮፕላኖች “የአገልግሎት ግዜያቸው አብቅቷል” ከተባለ በኋላ፤ በወረደ ዋጋ ለመከላከያ ድርጅት የርጥባን ያህል ተሰጥተዋል። በአየር መንገዱ ውስጥ ግልጽነት የለም። ማኔጅመቱ ወይም ሌላ የስራ ሃላፊ ሊሰራ የሚገባውን ነገር፤ ተወልደ በጎን ተነጋግሮ የሚሊዮን ዶላር ጉዳይ በጓሮ በር ሲያስጨርስ ይታያል። በምሳሌ ላይ ሌላ ምሳሌ ማቅረብ እንዳይሆንብን እንጂ ሌላም ጉዳይ እዚህ ላይ ማከል ያስፈልጋል።

 

አብዛኞቹ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ቦይንግ አውሮፕላኖች የኢትዮጵያ አይደሉም። ይልቁንም ከሌላ አገር በኪራይ መልክ የሚሰራባቸው ናቸው።  ጨዋታውን ልብ ብለው ይከታተሉ። በቅድሚያ አየር መንገዱ ለቦይንግ የስራ ትእዛዝ ይሰጣል። (የአንድDreamliner ዋጋ እስከ 200 ሚሊዮን ዶላር መሆኑን ልብ ይበሉ።) አውሮፕላኖቹ ተሰርተው ሲያልቁ፤ ሌላ ነጋዴ ድርጅት አውሮፕላኑን እንዲገዛው ይደረግና ለሃያ አመታት መልሰን እንከራየዋለን። ነገሩን በቀላሉ ለማስረዳት… ለምሳሌ ባለፈው ወር AWAS የተባለው የአየርላንድ ድርጅት ሶስት 787-8 Dreamliner ከኢትዮጵያ አየር መንገድ ገዛ። ግዢውን የፈጸመበት የፊርማ ቀለም ሳይደርቅ፤ እነዚያኑ አውሮፕላኖች መልሶ ለኢትዮጵያ አየር መንገድ አከራየው።

አንዳንዶች “ምን የሚሉት አሰራር ነው?” ይሉ ይሆናል።

 

በዚህ ጉዳይ… አየር መንገዱ መልስ እንዲሰጥ ቢጠየቅ፤ “ይህ የኛ ቢዝነስ ስትራቴጂ ነው” የሚል የተለመደ  መልስ አለው። ነገር ግን ከዚህ ጀርባ ሊኖር የሚችለውን የጓዳ በር ገንዘብ ቅብብሎሽ ከነተወልደ በቀር አየር መንገዱም አያውቀውም። ልብ ይበሉ። AWAS የተባለው የአየርላንድ ካምፓኒ የአንድ ቤተሰብ የግል ሃብት ነው። ግለሰብ እና የአየር መንገድ ስራ አስኪያጅ መለኪያቸውን እያጋጩ የሚያወጡትን እቅድ፤ ከህወሃት እና ከነተወልደ በቀር አየር መንገዱ ዝርዝር ጉዳዩን ሊያውቀው አይችልም። በነገራቹህ ላይ… ከኢትዮጵያ ንተገዝቶ ለኢትዮጵያ የሚከራየው አውሮፕላን በሃያ  አመት የኪራይ ዘመኑ ወቅት፤ አውሮፕላኑ ቢበላሽ የጥገናውን ወጪ አከራዩ ሳይሆን የኢትዮጵያ አየር መንገድ ነው የሚሸፍነው።

ተወልደ ምላሽ ሰጠ፤ “በየሰፈሩ ለተደራጁ ወጣቶች ከጽዳት እስከ ሻንጣ ጎታች ድረስ ስራ እንዲቀጠሩ አደርጋለሁ።” አለና ተጨበጨበለት።

 

በሚቀጥለው ቀን… እንዳለው አደረገ። በሚገርም ሁኔታ ቀደም ሲል በኮንትራት የተቀጠሩት ሰራተኞች በሙሉ ያለምንም ማስጠንቀቂያ ተባረሩ።  በነሱ ምትክ ስለስራው ምንም የማያውቁ፤ በየመንደሩ ተደራጅተው ለኢህአዴግ የሚያሳብቁ፤ የወጣት ሊግ አባላት ኤርፖርቱን ሞሉት። ሻንጣ ተሸክሞ ማውረድ፤ አውርዶ መጎተት፣ ጎትቶ መጫን ከባድ ሆነባቸው። የመንገደኛው ሻንጣ በአግባቡ ባለመጫኑ፤ አውሮፕላኖች ከመንሻ ሰአታቸው እያረፈዱ… Delay በ delay ሆኑ። ይህ ቀን በአየር መንገዱ ሰራተኞች ብቻ ሳይሆን፤ በመንገደኛውም ጭምር የማይዘነጋ ሆኖ አለፈ።

በመጨረሻ… ከቀድሞዎቹ ሰራተኞች አንዳንዶቹ ወደ ስራ እንዲመለሱ ተደርጎ፤ የወጣት ሊግ አባላቱን አለማመዷቸው። እነዚያ ከየሰፈሩ እንደ ንፍሮ ተዘግነው የመጡ ወጣቶች፤ አንዳንዶቹ ሲቀሩ አብዛኞቹ ቀስ በቀስ ስራው እየከበዳቸው ወደቀድሞ የማሳበቅ ስራቸው ተመለሱ። እግዜር በቸርነቱ እንደደመና በተናቸውና ጥቂት ወጣቶች ብቻ በዚህ ስራ ቀጠሉበት። ይሄን እንደምሳሌ ያነሳነው ተወልደ ወልደማርያም በማናለብኝነት የሚፈጽመውን ብልሹ አሰራር ለመግለጽ ያህል ነው።

 

ሌላም ነገር እንጨምር። ተወልደ ስልጣን ከያዘ በኋላ፤ ሰራተኞች የሚሞሉት ቅጽ ተላለፈ። በቅጹ ላይ ሰራተኞች ብሄራቸውን፣ ማንነታቸውን እና የየትኛው ፖለቲካ ድርጅት አባል ወይም ደጋፊ እንደሆኑ የሚጠይቅ ቅጽ ተሰራጭቶ የአየር መንገዱ ሰራተኞች እንዲሞሉ ተደረገ። አሁን ታዲያ የስራ እድገትም ሆነ ንፍገት ሲያስፈልግ፤ ያቺ የሞሏት ቅጽ ካለችበት ትወጣና… የሰራተኛው ማንነትና ብሄሩ እየታየ ወደላይ ያድጋል ወይም ወደ ታች እንዲወርድ ይደረጋል። በ’ርግጥ ይህ አይነቱ አሰራር በአንዳንድ ትላልቅ ድርጅቶች ውስጥ የሚታይ ቢሆንም፤ በአየር መንገዱ ውስጥ እየጎላ የመጣ ችግር ሆኗል። እንዲህ አይነቶቹን የአስተዳደር ችግሮ አውርተን ስለማንጨርስ ወደ Dreamliner 787 ጨዋታችን እንመለስ።

 

ቀደም ሲል በነበረው አሰራር፤ ለአውሮፕላን ስም ሲወጣ የህዝብ ግንኙነት ክፍል ሰራተኞች ዝርዝር ስሞችን ለተወልደ ያቀርቡለትና ውሳኔውን እሱ ይሰጣል። አሁን ግን… በምን መስፈርት አዲሱ Dreamliner  በመለስ ዜናዊ ስም እንዲሰየም እንዳደረጉ ማንም አያውቅም። ምናልባት የህዝብ ግንኙነት ክፍሉም ይህን ስም ለተወልደ አላቀረበም ይሆናል። ድንገት በመለስ ስም አውሮፕላኑ ሲገባ ግን ሁሉም ደንግጠዋል።

 

በመለስ ስም  አውሮፕላን እንደሚገባ ሰራተኞች የማያውቁትን ያህል፤ የአውሮፕላን ግዢ ሊዝ አፈጻጸሙን  ስራ አስኪያጁ ተወልደ እና የቅርብ ሰዎች ካልሆኑ በስተቀር ሌሎች በጉዳዩ ላይ አይመክሩበትም። የዛሬው ጨዋታችን ላይ ምሳሌ ማቅረብ አብዝተናል። ቢሆንም “ለምሳሌ” ብለን ለምሳሌ ብለን ጨዋታችንን እንቀጥል። ለምሳሌ አሁን ኢትዮጵያ ውስጥ ካሉት Dreamliner ውስጥ መጀመሪያ የገቡት 5 አውሮፕላኖች ፍጥነት እና ድሎታቸው ተደማምሮ፤ “የተገዙበትን ዋጋ ይመጥናሉ” ብለን እንለፋቸው። ቀጥሎ የገቡት አራቱ “ደህና ናቸው” እንበል። አሁን (በመለስ ስም የተሰየመውን ጨምሮ) ወደ ኢትዮጵያ እየገቡ ያሉት ስድስት አውሮፕላኖች ግን፤ ከጀርባቸው ሙስና ከሌለ በቀር አትራፊ አይደሉም። በመረጃ እንነጋገር።

 

አሁን ወደ ኢትዮጵያ እየገቡ ያሉት ስድስት Dreamliner  787 አውሮፕላኖች… ቦይንግ ለሙከራ ሰርቷቸው የነበሩ ናቸው። በ2011 ተመርተው፤ ለጃፓኑ ANA አየር መንገድ ለሙከራ ተሰጡ። ሆኖም አውሮፕላኖቹ Boeing የዲዛይን specification ላይ ያለውን የክብደት መጠን (Delivery Empty Weight) የማያሟሉ ስለሆኑ የጃፓኑ ANA “አልፈልጋቸውም” ብሎ ለቦይንግ ካምፓኒ የመለሳቸው ናቸው። የድሮ ዋጋቸው 150 ሚሊዮን ዶላር ሲሆን፤ ባለባቸው እንከን ምክንያት ዋጋቸው በጣም ዝቅ ተደርጎ እያንዳንዳቸው በ80 ሚሊዮን ዶላር የተገዙ ናቸው። (መጨረሻቸውን ያሳምረው እንጂ፤ ዋጋቸው ደህና ነው)

 

ጠቅለል ለማድረግ ያህል… አየር መንገዱ 15 Dreamlineሮች አሉት። አሁን እየታደሱ የሚገቡት ስድስቱ ላይ፤ የጃፓኖቹን ያህል ባይሆንም ከትርፍ አኳያ፤ ጥናት ተደርጎ ለስራ አስኪያጁ ተወልደ ወልደማርያም ሰነዱ ተሰጥቶታል። በዚህ ጥናት ላይ የቦይንግ 767 እና 787ንፅፅር ተደርጓል። ንፅፅሩ የተደረገው ተሳፋሪ እና ጭነት የመሸከም አቅማቸው በሂሳብ ተሰልቶ፤ ከDreamlineሮቹ ይልቅ አየር መንገዱ መጨረሻ ላይ የገዛቸው ሶስት 767 አውሮፕላኖች የተሻሉ መሆናቸውን ባለሙያዎች ስሌቱን ሰርተው፤ ሰነድ አደራጅተው ለበላይ አካል አቅርበዋል። ይህ ሁሉ ጥናት ተደርጎም፤ ደረጃቸውን ስላላሟሉ ለቦይንግ የተመለሱት ስድስት አውሮፕላኖች፤ ቀለማቸው ተቀይሮ ወደ ኢትዮጵያ ገብተዋል። የአስተዳደሩን ብልሹነት ማሳያ እንዲሆን በሚመስል መልኩ፤ 13ኛውን አውሮፕላን Meles የሚል ስያሜ ሰጥተውታል። ሌላ ሁለት የሚገቡ አሉ። “የነሱ ስም ደሞ ማን ይሆን?” በማለት፤ “አዜብ ወይም ኃይለማርያ ደሳለኝ ይሏቸው ይሆን?” እያልን በጭንቅ አለን።

 

በኢትዮጵያ አየር መንገድ ውስጥ ከሚታዩት የዘረኝነት እና የአስተዳደር ብልሹነት ባሻገር፤ ግልጽ ያልሆኑ አሰራሮች ይስተዋላሉ። ቸልተኝነት በጣም እየታየ ነው። ለምሳሌ የጥገና ሰራተኞችን ክፍል ብንመለከት… ከቅርብ ግዜ ወዲህ የሚቀጠሩት የጥገና ሰራተኞች ወደስራ ሲሰማሩ፤ ስራውን የሚያሳያቸው ወይም የሚያስተምራቸው ሰው በሌለበት ለአውሮፕላን የሚያደርጉት ክትትል እና ጥገና ደረጃውን የጠበቀ አይደለም። አንዳንዴ በተራ የሜካኒክ ቸልተኝነት (Human error) ምክንያት በሚሊዮን የሚቆጠር ዶላር ይባክናል – ይሄ ሁሉም የሚያውቀው የአየር መንገዱ ኪሳራ ነው።

 

ማጠቃለያውን ለማጠቃለል ያህል… በየአመቱ “አየር መንገዱ አትራፊ ነው።” ከሚል ዜና ውጭ ውስጡን የሚመረምር “ተው ባይ” የሌለበት፤ የአንድ ብሄር እና ድርጅት አባላት የገዘፈበት መስሪያ ቤት እየሆነ መጥቷል – የኢትዮጵያ አየር መንገድ።

ይህ ብቻ አይደለም። ባለስልጣኖች ለአስቸኳይ ጉዳይ ወይም ህክምና ወደደቡብ አፍሪቃ፣ እና ኤዥያ መሄድ ሲፈልጉ በአየር መንገዱ ወጪ ቻርተር አውሮፕላን ተዘጋጅቶላቸው ይሄዳሉ፤ ይመለሳሉ።

 

እናም ከምንሳፈርበት አውሮፕላን ጀርባ፤ ይህንና ይህን የመሳሰሉ ታሪኮች አሉ። እዚህ ላይ ለመጥቀስ የተሞከረው እጅግ በጣም ጥቂቱ ጉዳይ ነው። ወደ ውስጥ ገብቶ ጉዳዩን ለሚከታተል ሰው፤ የአየር መንገዳችን ነገር “ውስጡን ለቄስ” የሚያሰኝ ነው። አሁን መለስ የሚል አውሮፕላን ገባ። ነገ ከነገወዲያ ደግሞ በነአዜብ እና ሳሞራ ስም የሚሰየሙ አውሮፕላኖች ሊመጡ እንደማይችሉ ምንም ዋስትና የለም።

 

ወጋችንን የምናጠናቅቀው ስለኢትዮጵያ መርከቦች ጥቂት ነገር ብለን ነው። ከዚያ በፊት ግን አቶ ግርማ ዋቄ የቀድሞው የአየር መንገዱ ስራ አስኪያጅ የስንብት ንግግር ሲያደርጉ ያሉትን እናጋራቹህ። “እስካሁን በነበረኝ ቆይታ መንግስት ጣልቃ ሳይገባብን፤ ስራችንን በነጻነት እንድንሰራ ስለተደረገ ምስጋናዬን አቀርባለሁ። ወደፊትም አየር መንገዱ ከፖለቲካ እና ከመንግስት ተጽእኖ ውጪ ሆኖ እንዲሰራ እመኛለሁ።” ሲሉ ሰራተኛው ከዳር እስከዳር በጭብጨባ ነበር ያጀባቸው። በመጨረሻም ሰራተኛው ገንዘብ አዋጥቶ የገዛላቸውን አዲስ ኒሳን መኪና እየነዱ ነው አየር መንገዱን ተሰናብተው የወጡት።

 

አቶ ግርማ ዋቄ በተለይ የሚታወቁት “ቪዥን 2025” በሚል ባወጡት የአየር መንገዱ የረዥም ግዜ እቅድ ነው። አሁን አየር መንገዱ እየተገበረ ያለው የአቶ ግርማ ዋቄን የ15 አመት እቅድ ሲሆን፤ “ልጆቼ ከፖለቲካ ነጻ ሆናቹህ ስሩ” ያሉትን አደራ ግን – እነተወልደ የሚጋሩት አይነት አይመስልምም።

ከላይ እንደገለጽነው… የኢትዮጵያ መርከብ ድርጅት ጉዳይ አንስተን በዚሁ እንለያይ። እንደኢትዮጵያ አየር መንገድ ሁሉ የኢትዮጵያ መርከብ ድርጅት በተመሳሳይ የዘር ባህር ላይ እየተንሳፈፈ ይገኛል። እንደታወቀው ቀይባህር ለኤርትራ ከተሰጠ ወዲህ “ለኢትዮጵያ መርከብ አያስፈልጋትም” ተብሎ፤ ያሉት በቁማቸው ተሸጡ። አንዳንዶቹም ስማቸውን ለወጡ። እነአባይ፣ ሰላም እና አንድነት የሚባሉት የንግድ መርከቦች አሁን በሌላ ተተክተዋል። አሁን ኢትዮጵያ ካሏት 11 የንግድ መርከቦች መካከል ዘጠኙ የተገዙት በ2013 ላይ ነው። ሁሉም የከተማ ስያሜ ተሰጥቷቸዋል። ጋምቤላ፣ ባህርዳር፣ ሀዋሳ፣ ሃረር፣ መቐለ፣ ሰመራ፣ ጅጅጋ፣ አሶሳ የሚባሉ መርከቦች አሉን። በኢትዮጵያ እና አፍሪቃ መዲና – አዲስ አበባ ስም የተሰየመ አንድ መርከብ ቢኖር… እሱንም ፊንፊኔ ተብሎ እንዲጠራ ነው የወሰኑት። እንደው አንዳንዱ ድርጊት “መንግስት ነኝ” ከሚል አካል የማይጠበቅ ስለሆነ እንደምሳሌ አነሳነው እንጂ፤ አዲስ አበባ ራሷ ዋስትና ያጣች ከተማ ሆና የለችምን?

እንደው “ኢህአዴግ የተፈጠረው የአዲስ አበባ ልጆችን ለማናደድ ነው” የሚለውን ለማረጋገጥ ካልሆነ በስተቀር፤ ለአዲስ አበባ የመርከብ ስም መንፈግ አስፈላጊ አልነበረም።

ቸር ያሰማን።

 

 

በደብረ ታቦርና ለፋርጣ ሕዝብ ጥሪ እየተበተነ ነው

$
0
0

በከተማዋ የተለያዩ አካባቢዎች የቅስቀሳ ወረቀቶች እየተለጠፉ ነው። የወልቃይት ጠገዴ ዐማሮች ጉዳይ ዋነኛ የዐማራ ተጋድሎ ማዕከል ነው።
ስለ መተከልና ራያ ዐማሮች ስቃይ በቅስቀሳ ወረቀቶቹ ላይ በዝርዝር ተዘጋጅቷል።
ቀጥሎ የምትመለከቷቸው የቅስቀሳ ማስታወቂያዎች በደብረታቦር ከተማ የተለጠፋና በመለጠፍ ላይ ያሉ ናቸው።

debertabor

debrtabor

ነገ ጥዋት በቅድስቷ እየሩሳሌም ታላቅ የሰላማዊ ሰልፍ ጥሪ ከ10 ሰዓት ጀምሮ በእስራኤል ፓርላማ ፊት ለፊት!! ላልደረሰው እንዲደርስ ሸር በማረግ ይተባበሩን

$
0
0

Jerusalem demo696940_n

ነገ ጥዋት በቅድስቷ እየሩሳሌም ታላቅ የሰላማዊ ሰልፍ ጥሪ ከ10 ሰዓት ጀምሮ በእስራኤል ፓርላማ ፊት ለፊት!! ላልደረሰው እንዲደርስ ሸር በማረግ ይተባበሩን

x

Viewing all 15006 articles
Browse latest View live