Quantcast
Channel: Ethiopian News | ዘ-ሐበሻ | Latest News Provider | News For All
Viewing all 15006 articles
Browse latest View live

ኢትዮጵያ የፌደራል ሥርዓትን የምትከተል አገር አይደለችም – ገለታው ዘለቀ

$
0
0

 

federalismኢትዮጵያ ሆይ የአስተዳደር ዘየሽ ምን ይመስላል?  ተብላ ብትጠየቅ በዓለም ላይ የፌደራል ስርአትን ከሚከተሉ  አገራት አንዷ ነኝ ስሜም የኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ መንግስት ይባላል ትላለች። በርግጥ በዓለም ላይ ካሉ ብዙዎቹ ሃገራት የፌደራል ስርአትን አይከተሉም። ብሪታኒያን ፈረንሳይን  ጨምሮ በዴሞክራሲ የበለጸጉ አንዳንድ አገራት የአሃዳዊ አስተዳደር ዘየን ይከተላሉ። በአንፃሩ የፌደራል ስርአትን የፈጠረችውን የተባበረችውን አሜሪካንን ጨምሮ አውስትሬሊያ ካናዳና ብራዚልን የመሳሰሉ አገሮች የፌደራል ስርአትን ይከተላሉ። እንግዲህ ታዲያ አሃዳዊ ስርአትን የሚከተሉም ይሁኑ ወይም የፌደራል ስርአት የሚከተሉ እንዳንዶች ዴሞክራት አንዳንዶች ደግሞ ገና ዴሞክራሲ ያላደገባቸው ሆነው ይታያሉ። ብቻውን አሃዳዊ ወይም ፌደራላዊ መሆን ለዴሞክራሲም ለመልካም አስተዳደርም  ዋስትና አይሆንም። መሪዎች የፓለቲካ ቁርጠኝነት ከሌላቸውና የዴሞክራሲ ባህል ካልዳበረ ጥሩ የአስተዳደር ስርአት ብቻውን ፋይዳ የለውም። በርግጥ ለዴሞክራሲ ስርዓት የቆረጡ ፓለቲከኞች ደግሞ ለዴሞክራሲ ስርዓት ማንሸራሸሪያ የሚሆን የተሻለ ሲስተም መፍጠር አለባቸው። ስርአት ብቻውን ምንም አይሰራም እንበል እንጂ ከዴሞ ክራሲ ጋር ሆኖ አንድ ስርአት ከሌላው የተሻለ ውጤት ሊያመጣ ይችላልና ከስርአት ስርአት መምረጥ ተገቢ ነው። ለምሳሌ በአሁነ ሰአት ያለው የኢትዮጵያ ችግር የመንግስት ለዴሞክራሲ መዳበር አለመቁረጥ ብቻ ሳይሆን የሲስተም ችግርም አለው። ሲስተሙ ዴሞክራሲን እንዴት እየጠለፈ እንደሚጥለው ወደ ኋላ ላይ በስፋት እናያለን።

 

ወደ ኢትዮጵያ የመንግስት አወቃቀር እንመለስና በርግጥ ኢትዮጵያ በአሁኑ ሰአት ፌደራል ነኝ እንደምትለው በርግጥ የፌደራል ስርአትን እየተከተለች እንደሆነ ልንፈትሻት ይገባል። በመሰረቱ አንድ አገር የፌደራል ስርአትን መርጫለሁ ሲል የፌደራል ስርአትን የፍልስፍና መሰረቶች አምኜባቸዋለሁ ተግባራዊ እያደረኳቸው ነው ማለቱ ነው። ኢትዮጵያ በርግጥ የፌደራል ስርአትን መከተል አለመከተሏን ማሳያ ከሚሆኑት የፌደራሊዝም ባህርያት ጋር እያገናዘብን መገምገም አለብን። ለመሆኑ የፌደራል ስርአት መገለጫዎች ምን ምን ናቸው?

 

የሃይል ክፍፍል

 

ከብዙ አመታት በፊት አሜሪካውያን አንድ የእስተዳደር ዘየ በራላቸው። የዚህ ዘየ ፍልስፍና መነሻ ሃይልን በፓለቲካ ዩኒቶች መሃል በመከፋፈል መንግስትን ራሱን በመዘርዘር ሰፊ ለሆነችው አሜሪካ መልካም አስተዳደርንና ዴሞክራሲን የበለጠ እናራምዳለን የሚል ነበር። ከመነሻው አሳቡ የመነጨበት ስነ ልቡና ዴሞክራት እንደሆነ መረዳት ይቻላል። ስልጣንን ማጋራትና ወደ ህዝብ ቀረብ ማድረግ ለአምባገነን መሪዎች አስፈሪ ቢሆንም እነዚያ የአሜሪካ ቆራጥ የዴሞክራሲ አርበኞች ግን ስልጣንን በማካፈል የተለየ አስተዳደር ለማምጣት ቀዳሚ ሆኑ።

 

የፌደራሊዝም አሳብ የያዘው ተልእኮ በአንድ የፓለቲካ መዋቅር ውስጥ በዋናነት ሁለት መንግስታት ተመስርቶ የፌደራልና የስቴት መንግስታት ተፈጥረው እነዚህ ሃይላት የራሳቸው ህገ መንግስት ኖሯቸው ነገር ግን ከዋናው የሃገሪቱ ህገ መንግስት ጋር የማይጣረስ ሆኖ መኖር ለዜጎችም ምርጫን ይጨምራል መልካም ፍክክርን ያመጣል ቅልጥፍና ያመጣል ከሚል ነው። ክልሎች የመለስተኛ አገር ያህል ስልጣን ይዘው የሚሰሩበት ሁኔታ ተፈጠረ ማለት ነው።  በአሜሪካ ሁኔታ ሃምሳ መንግስታት ተፈጠሩ ማለት ነው። መንግስት የሚለው ጽንሰ ሃሳብ ተዘረዘረ ማለት ነው። በተለምዶ አንድ ጠቅል መንግስት የነበረውን ወደ ሃምሳ መንግስታትን የያዘ አንድ የፌደራል መንግስት ተፈጠረ ማለት ነው። መንግስት ሃይሉን ዘርዝሮ ሲሰራበት የበለጠ ያተርፋል። የበለጠ ይወልድለታል። የህግ ሪሶርሶች ይጨምራሉ። የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤቶች ይበዛሉ። ተመሳሳይ ችግሮች በተለያየ ክልል ምክር ቤት ሲታዩ የተሻለ ምርጥ አሳብ ለማግኘት ይረዳል። በብዙ ጠረንጴዛ ዙሪያ የሚደረግ ውይይት የክልልንም የሃገርንም ችግር ለመፍታት ትልቅ ሃይል ነው። የህዝብን ተሳትፎ ከፍ ያደርጋል።ለፌደራል መንግስት የማሰቢያ ጊዜ ይሰጠዋል።

 

አንዱ ሌላው የዚህ የፌደራል ስርአት ፍልስፍና መነሻ ስልጣን አካፈልን ማለት ሃላፊነትን ማካፈል ማለት ነው። ሃላፊነትና ስልጣን አብረው የሚሄዱ የአንድ ሳንቲም ሁለት ገጽታዎች ናቸው። ሃላፊነትን አንድ ቦታ ከመከመር ይልቅ ማከፋፈሉ ፈጠራን መነቃቃትን የያገባኛል ስሜት (sense of belongingness)  ሁሉ ይጨምራል። የልማት የመልካም አስተዳደር ሃገር የመምራት የሰላም ጉዳዮች ሃላፊነትን ዘርዘር ስናደርግ የበለጠ ምርታማ ይሆናሉ ከሚል ይመስላል።  በዘመኑ አገላለጽ የብዝሃነት አስተሳሰብ ውጤትም ነው።

 

በዚህ መሰረት አንድ ሃገር የፌደራል ስርአት ተከታይ ነኝ ካለ የሚጠየቀው ዋና ጥያቄ ሃይል አካፍለሃል ወይ? ሃላፊነትን አካፍለሃል ወይ? የሚል ነው የመጀመሪያው ጥያቄ። እውነተኛ የሃይል  ክፍፍል ከሌለ እውነተኛ ፌደራሊዝም የለም። እውነተኛ የፌደራል ስርአት ከሌለ ደግሞ አለ እያሉ ማውራት ከቶ ለምን ይጠቅማል?

 

ይህን የሃይል ክፍፍል እንደ ዋና የፌደራል ስርአት መገለጫ አድርገን የኢትዮጵያን የሃይል ክፍፍል መገምገም አለብን። ይህ ግምገማም በርግጥ ኢትዮጵያ የፌደራል ስርአትን እየተከተለች ነው ወይ?  የሚለውን ፍንትው አርጎ ያሳየናል።

 

በፌደራል ስርአት ምስረታ ጊዜ ክልሎች የራሳቸው ህገ መንግስት ይኖራቸዋል። ይህ ህገ-መንግስት ስልጣናቸውን ተግባራዊ የሚያደርጉበት መሳሪያ ነው። በርግጥ ኢትዮጵያ እነዚህ የክልል ህገ መንግስታት ያሏት ሲሆን የፓለቲካው እውነተኛ ሃይል ግን በከፍተኛ ሁኔታ በፌደራል አካባቢ ተከምሮ ይታያል። ይህ የስልጣን ክምር በአብዛኛው ባልተፃፈ ህግ የተዘረፈ ነው።

 

እንደሚታወቀው የፌደራሉን መንግስት እመራለሁ የሚለው ኢህአዴግ  በሃይል በህወሃት ተጽእኖ ስር ወድቋል። ይህ ማለት የፌደራል መንግስቱ ሃይል በህወሃት አካባቢ ነው ማለት ነው። ከፍተኛ የጦሩ መሪዎች የሰኪዩሪቲ መሪዎች የዚህ ቡድን አባላት ሲሆኑ የፌደራሉን ተቋማት መሳሪያ እያደረጉ የሆነ ክብ ሰርተው የዚያን ክብ ኢኮኖሚያዊ አቅም ሲያጎለብቱ ይታያል። የክልል መንግስታት ሃይላቸውን ተገፈው በጣም የደከሙ ስለሆነ ህዝብ በተፈጠሩት ክልሎች ላይ እምነት አጣ። እውነተኛ የሃይል ክፍፍል ኖሮ ቢሆን እውነተኛ የፌደራል ስርአት ስለሚኖር የኦሮሞ ህዝብ በዚህ ደረጃ ባላመፀ። የአማራና የኦጋዴን የሌሎችም ክልሎች ህዝቦች ባላማፁ። ህዝቡ ቀድሞ ነገር የክልል መንግስታትን እንደ ህወሃት መጠቀሚያ ያያል። የህዝቡ እምነት (perception) የሚያሳየው እውነት ደግሞ ሃይል ሲበዛ በህወሃት እጅ ውስጥ መሆኑን ነው። የሚገርመው ነገር ከትግራይ ክልል ውጭ የየትኛውም ብሄር አብዛኛው አባል በተለይ ለሂቁ የቡድናቸው የፓለቲካ ባለስልጣን የህወሃት ቅጥረኛ ነው ብለው ያምናሉ። ኦሮሞዎች፣አማሮች፣ደቡብ ወዘተ ተመሳሳይ እምነት አላቸው። ትግራይ ላይ የሚለየው ነገር የትግራይ ህዝብ ህወሃትን የጠላው ይህ ድርጅት በሌሎች የፓለቲካ ቡድኖች ተጽእኖ አለበት ብለው ሳይሆን የሚያዝኑት ድርጅቱ ዴሞክራሲያዊ ባለመሆኑና ከባህላዊ እሴቶቻቸው የወጣ እሴቶቻቸውን ያላገናዘ በመሆኑ ከሌሎች ቡድኖች ጋር እያጋጨ እየጠቀምኩህ ነው ማለቱ ነው።  ይሉኝታውን ሸጦ ማሸማቀቁ  አገሩን ሲጎዳ ማየቱ ከወንድሞቹ ሁሉ ለማለያየት መጣሩ ትግራይን ጎድቶታል። ህወሃት ከአማራና ከኦሮሞ ከሌላውም ፈንታ ላይ እየዘረፈ እያመጣ ይሄውልህ ፋብሪካ ሰራሁልህ ይሄው መንገድ ሰራሁ አሁን ከሌሎች ክልሎች እኛ አንደኛ ወጣን………. የተሻለ ለምተናል ሲለው የትግራይ ህዝብ የበለጠ ይጎዳል ያፍራል ይመስለኛል። ይሉኝታ አብሮ መብላት ባህሉ የሆነው ትግራይ ይህ ቡድን ማፈሪያ ሆኖበታል።

 

ለማናቸውም ግን ይህ የትግራይን ህዝብ እወክላለሁ የሚለው ህወሃት የሃገሪቱን ስልጣን ስለጠቀለለ በተግባር የፌደራል ስርአት አለ ማለት አይቻልም ማለት ነው። ከፍ ሲል እንዳልነው እውነተኛ የሃይል ክፍፍል ከሌለ የፌደራል ስርአት የለምና። ኢትዮጵያ ይህን ሁሉ ሃይል ጠቅልላ ለአንድ ጎጠኛ ቡድን አስረክባ የፌደራል አገር ነኝ ብትል የሚሰማት የለም። ዋናው የፌደራል ስርአት የፍልስፍና መሰረትም የተፈጠረበት አላማም ይሄው ሃላፊነትንና ስልጣንን ማካፈል በመሆኑ ይህንን የከላ አገር ፌደራላዊ መንግስት ነኝ ለማለት ከቶውንም አይችልም።

 

 

ማንነት

 

አንዱ የፌደራል ስርአት ጥቅም እንደ ኢትዮጵያ ብዙ ዘውጎች ባሉበት አገር ዘውጋዊ ማንነትንና ብሄራዊ ማንነትን አጣጥሞ ለማራመድ ስለሚመረጥ ነው። ዘውጋዊ ማንነትና ብሄራዊ ማንነትን እንደ ተቃራኒ ማየት ለሃገር ኣደገኛ ነው። በኢትዩጵያ ሁኔታ ዘውጋዊ ማንነትንና ብሄራዊ ማንነትን በሚገባ ያልተረዱና ያላጠኑ የፖለቲካ ድርጅቶች ሃገሪቱን ወዳልሆነ አቅጣጫ ሊወስዷት ይችላሉ። በመሆኑም በሃገራችን ፖለቲከኞች ህይወት ውስጥ ኣንድ በጥልቀት ሊጠናና የፖለቲካ የፍልስፍና መሰረት ሊሆን የሚገባው ጉዳይ ይህ የብሄር ማንነትና የብሄራዊ ማንነት ጉዳይ ነው። ወደ ኋላ ታሪካችንን ስናይ አገራችን ኢትዮጵያን እነዚህን ሁለት ማንነቶች በሚገባ ያስተናገደችበት ጊዜ የለም። ሁል ጊዜም እንደ ኣጥፊና ጠፊ በማየት ኣንዱ ኣንዱን እየረመረመ እንዲሄድ የሚደረግበት ሁኔታ ነው ያለው። የኢትዮጵያን ታሪክ ስናይ ብሄራዊነት የሚያብበው የብሄሮችን ማንነት በመደፍጠጥ መስሎ ስለታያቸው ለረጅም ጊዜ የብሄሮች ማንነት ተጎድቶ ብሄራዊ ማንነትን ለማፈርጠም ተሞክሯል። ይሁን እንጂ መዋጥ የሚሰማቸው ብሄሮች ማንነታችን ኣደጋ ላይ ነው በሚል ሲታገሉ ኖረዋል። ኢሃዴግ በ 1983 ዓ.ም ስልጣን ከያዘ በሁዋላ ደግሞ ብሄራዊ ማንነትን ጽንፍ ሄዶ በማራከስ ኣካባቢያዊ ማንነት እንዲያብብ ጥረት አድርጓል። በውጤቱም ዛሬ ብሄራዊ ማንነት በአካባቢያዊ ማንነት እየተረመረመ ይገኛል። ዘውጎች ሁሉ የፖለቲካ ጥብቋቸውን ለብሰው ለብሄራዊ ማንነት ጡንቻቸውን በማሳየት ኣንተ ምንድነህ? (ለመሆኑ ኢትዮጵያ ምንድናት እሷ?……..) እስኪሉ የድፍረት ቃል እስኪወጣቸው ብሄራዊ ማንነት ኮስሷል። ይህ ኣንዱ ባንዱ ላይ ጎልብቶ ለመታየት የሚደረግ ጥረት ሃገራችንን እንዳትራመድ ያደረገ፣ የዴሞክራሲ እድገታችን ጠላት ነው። ፖለቲከኞች ልንረዳው የሚገባው እነዚህ ሁለት ማንነቶች የማይገሰሱ የኢትዮጵያውያን መገለጫዎች ናቸው። ሁለቱም እርስ በርስ መረማመድ የለባቸውም። ማሸቀዳደምም ኣይገባም። አንድን ግለሰብ ከክርስትናህና ከኢትዮጵያዊነትህ የቱ ይበልጣል? የቱ ይከተላል? ብሎ መፈተን ተገቢ አይደለም። አንድ ዜጋ እነዚህን ሁለቱንም ማንነቶቹን ኣንደኛ ደረጃ ሰጥቶ እየወደዳቸው ሊኖር ይችላል። ቀድሞውንም ውድድር ውስጥ መግባት የለባቸውም። ልክ እንደዚህ ኣንድ ኦሮሞ ከኦሮሞነትህና ከኢትዮጵያዊነህ የቱ ነው መጀመሪያ? ሊባል ኣይገባም። ሁሉቱም ኣንደኛ ሁነውለት ሳይነቃቀፉ መኖር ይችላሉ። ዋናው ችግር የሚፈጠረው እነዚህ ማንነቶች ሁሉ ኣንድ የፖለቲካ ዮኒፎርም መልበስ ኣለብን ብለው ብቅ ሲሉ ነው። በሃይማኖት ላይ በፖለቲካ መደራጀት ሲጀመር ሃይማኖትና ብሄራዊ ማንነት በአንድ የፓለቲካ የመሮጫ መም ላይ ስለሚገናኙ እነዚህን ሁለት ማንነቶች እንደ ተፎካካሪ እንደ ባላንጣ እንድናያቸው ያደርጋል። ድጋፋችን ወደ አንዱ እንዲያዘም ያደርጋል። ኣገር ማለትም ብሄራዊ ማንነት በተፈጥሮው የሚቆምበት ዋና መሰረት ፖለቲካ በመሆኑ ብሄርና ሃይማኖት ፓለቲካ መሆን ሲያምራቸው ሁለቱም ማንነቶች ማለትም ብሄራዊ ማንነትና ቡድናዊ ማንነት በኣንድ የሩጫ መስመር ላይ ይገናኛሉ። በዚህ ጊዜ ነው ፍክክር የሚገቡት። ፍክክሩ ደግሞ መርህን እየጣሰ ስሜትን እያራገበ ስለሚሄድ የሃገራችንን ህልውና አደጋ ላይ ሊጥልብን ይችላል።  በመሆኑም እነዚህን ሁለት ማንነቶች ሳናሽቀዳድም ለመንከባከብ የሚያስችል ራሱን የቻለ ሲስተም ልንቀርጽ ይገባናል። ይህ ሲስተም ሁለቱ ማንነቶች ለየብቻ እንደ ተፈጥሮኣቸው የሚሮጡበትን ስርዓት የሚፈጥር፣ ሁለቱም ማንነቶች ለየብቻ የሚሮጡበትን የሩጫ መም የሚዘረጋ ነው። ያንን ስናደርግ ኣካባቢያዊ ማንነትና ብሄራዊ ማንነት እንደ ባላንጣ ሳይሆኑ እንደ ዋልታና ማገር ሆነው ኣገራችን የረጋችና የጸናች ትሆናለች።

 

እንደ ኢትዮጵያ ላሉ ብዙ ብሄሮች ላሏቸው አገራት የፌደራል ስርአት ግጭትን ለመቀነስና ማንነትን ለመጠበቅ ይረዳል ሲባል ብሄራዊ አንድነትንም ባህላዊ ማንነትንም መጠበቅን ያገናዘበ መሆን አለበት። በዚህ መሰረት የኢትዮጵያን የፌደራል አወቃቀር ስናይ ብሄራዊ አንድነትን ሊሰራልን የሚገባውን ፓለቲካዊ ማንነት ለብሄሮች ሰጥቶታል። በሌላ አገላለጽ ፌደራሊዝሙ የመነጨው ከብሄር ፓለቲካ ነው። ኢህአዴግ ግንባር ነው  የሚባለው። ውሁድ ፓርቲ ባለመሆኑ ብሄራዊ ማንነትን የሚሰራው በዚሁ የኮንትራት ውል በግንባርነት ተክለ ሰውነቱ ነው። ይህ በመሰረቱ ብሄራዊ ማንነት የሚባለውን ትልቅ የፓለቲካ ጠገግ ውሽልሽል ያደርገዋል። ፌደራሊዝም ሲሰራ ሁለቱንም ማንነቶች እንዲጠብቅ እንጂ ብሄራዊ ማንነትን በግንባር ኮንትራት አውሸልሽሎ ለአካባቢያዊ ማንነት ብቻ ማሰብ የፌደራልን ጽንሰ ሃሳብ ያፈርሳል። በኢትዮጵያ ውስጥ የብሄሮችን ማንነት ለመጠበቅ የሚያስችል የፌደራል ስርአት ዘርግቶ ነገር ግን ፓለቲካዊ ስብእናችንን በአንድ ብሄራዊ ጠገግ ስር ማሳደር ይኖርብናል። የአሁን ዘመን ፌደራሊዝም የወደቀው በተለይ ብሄራዊ ማንነትን መጠበቅ አለመቻሉ ብቻ ሳይሆን የቡድኖችን ማንነት ለመጠበቅም ፍትሃዊ የስልጣን ክፍፍል የለውምና በዚህ በኩልም ጤነኛ ቡድናዊ ማንነትን እንድናዳብር ለማድረግ አላስቻለንም።

ለምሳሌ ስዊዘርላንድን ብናይ በቋንቋ ማህበረሰብ ላይ የተመሰረት ክልል ፈጥራ ስትኖር ፓለቲካዋን ግን በአንድ ብሄራዊ ማንነት ስር ነው መስርታ የምትኖረው። ስዊዘርላንድ ውስጥ በዘር ላይ የተመሰረተ የፓለቲካ ድርጅት ማቆም በህግ ያስቀጣል። ወደ ሃገራችን ኢትዮጵያ ስንመጣ የኢትዮጵያ የክልል አፈጣጠር መስፈርት ምን እንደሆነ መመርመር ተገቢ ነው። የብሄር ፌደራሊዝም ችግሮች አለበት እየተባለ የሚተቸውን ትችት ለጊዜው እንተወውና ለመሆኑ የኢትዮጵያ የፌደራል ስርአት ወጥነት ያለው በብሄር ፌደራሊዝም የሚገለፅስ ነው ወይ? የሚለውን እንድናነሳ ያደርገናል። እንግዲህ ኢትዮጵያ ከ82 በላይ ብሄሮችን ይዛ ዘጠኝ ክልሎችንና ሁለት ልዩ ቻርተር ከተሞችን   አዋቅራ ቁጭ ብላለች። ይህን ስናይ 82 ብሄር ያላት ሃገርና የብሄር ፓለቲካን የምታራግብ አገር በዘጠኝ የከፈላትን ምስጢር ለማወቅ ያቋምጠናል። ኢትዮጵያ ፌደራሊዝሟ ግልጽ በሆነ የብሄር ፌደራሊዝም ይገለጽ ዘንድ ሁሉም ብሄሮች የክልል መንግስትነት ስልጣን ሊካፈሉ ይገባ ነበር። አንዱ ብሄር የራሱ ህገ መንግስት ያለው ይሆንና እንዱ ደግሞ የዞንነት ስልጣንን ይጋራል ሌላው ብሄር ደግሞ የልዩ ወረዳ ስልጣን ወደዚያ ይወረወርለታል። እውነተኛ የስልጣን ክፍፍል በሃገሪቱ አለመኖሩ ብቻ ሳይሆን ችግሩ በብሄሮች እኩልነት ዙሪያ የፍልስፍናና የአመለካከት መሰረታዊ ችግር እንዳለም ያሳያል። የብሄሮች እኩልነት መገልጫ እንዱ እኩል የስልጣን መጋራት ነበር። ሎጂኩ እንደዚያ ነው። ማንነትን መሰረት ያደረገ ፌደራል ስርአት ተፈጠረ ከተባለ ግልፅ መሆን አለበት። በቁጥራቸው አናሳ የሆኑትን እያሰባሰቡ አንድ ክልል የማድረግ ጨዋታ ከሆነ ሃረሪ ለምን ክልል ሆነች? ብለው ሰዎች በዚህ የፌደራል ስርአት ግልፅነት ላይ ጥያቄ ያነሳሉ። የሃረሪ ህዝብ ብዛት ከአቃቄ ክፍለ ከተማ ህዝብ ያንሳል፣ ከሲዳማ እጅግ ብዙ እጅ ያንሳል። ቢያንስ ዞን እንኳን አድርጉኝ እያለ ከሚታገለው ከኮንሶ ህዝብ በብዙ እጅ ያንሳል። ግን ክልል ነው። ሃረር ክልል የሆነው ባህሉን እንዲጠብቅ ነው አይባልም መቼም። ሁሉም ቡድኖች የሚኮሩበት ባህል አላቸውና። ሁሉም ቡድኖች  የሚጨበጡና የማይጨበጡ ባህሎች አሏቸው። ከዚህም በላይ የማንም ባህል ከማንም አይበልጥምም አያንስምም። የሲዳማ ህዝብ ጥያቄ የግልጽነት ጥያቄ ነበር። ይህ ብሄር በቁጥሩ ከትግራይ ከቤንሻንጉል ከአፋር ከጋምቤላ ህዝብ ሳያንስ ትግራይና እነዚህ የተዘረዘሩት ክልል ሆነው ሲዳማ ክልል መሆን አለመቻሉ ብዙ ሰው እንዳደናገረ ይኖራል። ሃምሳ ስድስት የሚሆኑ የደቡብ ብሄሮች አንድ ክልል ሆነው ሃረሪና አፋር ቤንሻንጉል እንዲሁ ክልል ሆነው ስናይ ፌደራሊዝሙን በብሄር ፌደራሊዝም ለመግለጽም ይቸግረናል። መንግስት የሚለው ሁሉም ብሄሮች የክልልነት ደረጃ ባያገኙም በዞንና በወረዳ ደረጃ የራሳቸውን መንግስት አቁመዋል ነው። ይሄ እንዝህላል መልስ ነው። መንግስት እንደሚለው ፓለቲካው በብሄር ላይ ስለቆመና አስተዳደሩ በጎጥ ስለሆነ የብሄር ፌደራለዝም እንበል ነገር ግን እኩልነት የሌለበት የብሄር ፌደራሊዝም ይባል እንደሆን አላውቅም።  ብዙ ብሄሮች የከረረ ጥያቄ የማያነሱት ለስርአቱ እውቅና ካለመስጠት ስሜት ነው እንጂ ፌደራሊዝሙ ይሄ ነው የሚባል ግልጽ ፀባይ (patern) የለውም በውነቱ።  ስለሆነም የዚህ የፌደራል ስርአቱ አፈጣጠር ራሱ ችግር አለበት ማለት ነው። መንግስት ብዙ ጊዜ የሚናገረው ቡድኖች ማንነታችውን አግኝተዋል የሚል ነው።  የሚገርመው ይህ ስርአት ልዩነትን በማስፋት በአንድ ጽንፍ እየተከሰሰ በሌላ በኩል ደግሞ በግድ የሆነ ምስለትም ይታይበታል። ለምሳሌ የወልቃይትን ህዝብ ጉዳይ ማየት በቂ ነው። ስለዚህ ፌደራሊዝሙ በሁለት በኩል ይታማል። አንደኛው ቡድናዊ ማንነትን ጠብቆ ከብሄራዊነትጋር ሳይጋጭ ለማስኬድ አልቻለም ልዩነትን እያራገበ ዜጎች ከብሄራዊ ማንነት ጋር ያላቸውን መጣበቅ እንዲላላ አድርጓል ግልፅነትና ወጥነት የለውም የሚል ሲሆን በሌላ በኩል ለባህል ምስለት ወይም ለማንነት መጥፋት ያጋለጠው ቡድንም አለ። ለዚህ ዋና መገለጫው የወልቃይት ህዝብ ጉዳይ ነው። ከፍ ሲል እንዳልነው ወልቃይት በሃይል ትግራይን መስሎ እንዲኖር የተፈረደበት ህዝብ ነው። ለዚህም ነው በአሁኑ ወቅት ይህ የወልቃይት ጥያቄ ከፍተኛ ንቅናቄ እያመጣ ያለው። በአጠቃላይ የአቶ መለስ የፌደራል ስርአት ምስለት ፣ ጽንፍ የወጣ ልዩነት፣ ብሄራዊና አካባቢያዊ ማንነቶች የሚጋጩበት፣ ግልጽ ያልሆነ የብሄሮች የስልጣን ክፍፍል በአንድ ጊዜ የሚታይበት አስገራሚ የመንግስት ስርአት ነው። ስለዚህ ፌደራሊዝሙ ማንነቶችን በመንከባከብ ረገድ ችግር የፈጠረ ስርአት ነውና ኢትዮጵያ የፌደራል ስርአት አራምዳለሁ ብትል ስህተት ነው።

 

 

 

 

 

 

 

 

 

 

 

 

ዴሞክራሲ

 

ሌላው የፌደራል ስርአት እምነት ዴሞክራሲን እንደ ልቡ ለማንሸራሸር የሚያስችል ሲስተም አለው ስለሚባል ነው። አንዱ የፌደራሊዝም ስርአት ጭንቀት ስልጣን ወደ ህዝቡ ጠጋ እንዲልና ዴሞክራሲያዊ መብቶች እንደልብ እንዲሰሩ ነው። በዴሞክራሲ ስርአት ውስጥ የዜጎች የመምረጥ የመመረጥ መብት፣የንብረት ባለቤትነት መብት ጉዳይ፣ የዜግነት መብቶች ጉዳይ በጣም የፌደራል ስርአት የሚጨነቅላቸው ጉዳዮች ናቸው። ኢትዮጵያ የፌደራል ስርአትን ተግባራዊ ለማድረግ ስትነሳ የቡድንንም የግለሰብንም መብት ለመጠበቅ በሚያስችል መሆን አለበት። ይሁን እንጂ የኢትዮጵያ የብሄር ፌደራሊዝም ካመጣቸው ችግሮች እንዱና ጉልሁ ጉዳይ ግዙፍ የዴሞክራሲ ክፍተት (a huge democratic deficit)  ማምጣቱና ለዜጎች የሃገር ባለቤትነት መብት እክል መፍጠሩ ነው። እንደሚታወቀው የኢትዮጵያ ብሄሮች ተዋልደዋል፣ በተለያየ የሃገሪቱ ክፍል ተበትኖ የሚኖረው ህዝብ ብዙ ነው። ለምሳሌ ያህል በኦሮምያ 11 ሚሊየን አማራዎች ይኖራሉ። በሚሊየን የሚቆጠሩ ኦሮሞዎች በአማራ፣በደቡብ፣ በቤንሻንጉል ጉሙዝ በሃረሪና በሌሎችም ክልሎች ይኖራሉ። ብዙ ጉራጌዎች ከክልላቸው ውጭ ይኖራሉ።  የብሄር ፓለቲካ የወለደው ይህ የኢትዮጵያ የፌደራል ስርአት ያመጣው ችግር የነዚህን እጅግ ብዙ ዜጎችን የፓለቲካና የዜግነት መብታቸውን እንዲያጡ አድርጓል። ስለ ህዝብ መብት እጨነቃለሁ የሚለው መንግስት በዚህ የፌደራል ስርአት ለዲሞክራሲያዊ መብት ድርቅ ያጋለጣቸው ዜጎች ብዛት እጅግ አያሌ ነው። በኦሮምያ የሚኖረው አማራ ብቻ በቁጥሩ አሁን ያሉትን የአምስት ክልሎች ህዝብ ማለትም የአፋርን፣የትግራይን፣የሃረሪን፣የቤንሻንጉልን፣የጋምቤላን ህዝብ ተደምሮ ይበልጣል።ይሄ ሁሉ ህዝብ ሲስተሙ በፈጠረው የዴሞክራሲ ክፍተት ብቻ ፓለቲካዊና የዜግነት መብቶቹ በሃይል ይሰበራሉ።  ከክልሉ ውጭ የሚኖረው የኦሮሞ ህዝብ ከብዙ የደቡብ ብሄሮች ይበልጣል። እንግዲህ ሲስተሙ የዚህን ሁሉ ህዝብ መሰረታዊ የዴሞክራሲ መብቶች እንዲጣሱ ያደርጋል። አንዱ የኢትዮጵያ የመንግስት ስርአት ትልቅና መሰረታዊ ችግር ይሄ ነው።

 

የብዙዎችን ትኩረት ወደሚስበው ወደ የሃረሪ ክልል ጉዳይ ልመልሳችሁ። ሃረሪ ክልል የኢትዮጵያ የፌደራል ስርአት የዴሞክራሲን ችግር፣ የግልጽነት ችግር፣ አጠቃላይ የኢትዮጵያን ፌደራል ስርአት ቅጥ ማጣት  በተምሳሊት ቁልጭ አድርጋ የምታሳይ ክልል ናት።  በዚህ ጉዳይ ላይ ከዚህ በፊት በኢትዮጵያ ሳተላይት ቴሌቪዥን በኢትዮጵያ ነገ ፕሮግራም ላይ ዶክተር ሰለሞን ጋሻው ከአቶ ግዛው ለገሰ ጋር ያደረጉት ውይይት እጅግ መሳጭ ነበር። በዚህ ጽሁፍ ውስጥ ተጨማሪ አሳብ መስጠቱን መረጥኩ።

 

እንግዲህ ሃረሪ የቆዳ ስፋቷ 334 ኪሎ ሜትር ስኩየር ያህል ሲሆን 183,415 የሚሆኑ ወንድና ሴት ኢትዮጵያውያንን ይዛለች። ከአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ በህዝብ ብዛት ታንሳለች።   ሃረሪ ካሏት ህዝብ መካከል 56.4% ኦሮሞዎች፣  22.7% አማራዎች፣ 4.3%  ጉራጌዎች፣ 1.53 %  ትግሬዎች፣ 8.65%  ሃረሪዎች፣  1.26%  አርጎባዎች ናቸው::  ይህ ክልል ሲዋቀር ከሃረሪ ከተማ በተጨማሪ አስራ ዘጠኝ  ወረዳዎች ከኦሮምያ ተጨምረውበት እንደሆነ በዚህ ዙሪያ ጥናት ያካሄዱ ባለሙያዎች ይገልጻሉ። የኦሮሞው ቁጥር በአንደኛነት የበዛው ከአጠቃላዩ የህዝብ ብዛት ከግማሽ በላይ የሆነው እነዚህ ቀበሌዎች ስለተጨመሩ ነው ማለት ነው። በዚህ ክልል አወቃቀር ጊዜ ምንም ተጠይቅ የማይታይ ብቻም ሳይሆን የሚገርምም ነው። የክልሉ ባለቤት የሆነው 8.65% የሚሆነው ህዝብ ሲሆን 91% በላይ የሆነው ህዝብ የዚህ ክልል ዋና ባለቤት አይደለም። የመገንጠል አሳብ ቢመጣ እነዚህ ወደ ዘጠኝ በመቶ የሚሆኑ ወገኖች ብቻ ናቸው የሚወስኑት ማለት ነው?። ዋና ባለቤት ማለትስ ምን ማለት ነው?  ከዘጠና አንድ በመቶ በላይ የሆኑት ኢትዮጵያውያን መንግስት እንደሚለው መጤ ናቸው እንዳይባል ሃረር ላይ የተጨመሩት አስራ ዘጠኝ ቀበሌዎች ከኦሮሞ ክልል በመሆኑ እነዚህ ኦሮሞዎች መጤ አይባሉም ማለት ነው። ምክንያቱም ኦሮሞዎቹ ከተፈጠሩበት ቦታ ከነአፈራቸው ነው ወደ ሃረሪ የተከለሉትና በምን ሂሳብ ኦሮሞዎች በዚህ ክልል ውስጥ እንደመጤ እንደሚታዩ በተለይ ግልጽ አይደለም።  በዚህ ክልል  ስናይ ዘጠና አንድ በመቶ የሚሆነው ህዝብ የባለቤትነት ስሜት እንዳይኖረው ሲደረግ በአለም ያልታየ ከፍተኛ የዜግነትን መብት የጣሰ ጉዳይ ይሆናል።  ይህ ክልል የሚኖረው እነዚህ ዘጠና አንድ በመቶ በሚሆኑ ህዝቦች እውቀት፣ ጉልበት፣ ታክስ ነው። እነዚህ ህዝቦች ባለቤትነት መነፈጋቸው በተለይም ኦሮሞዎቹ በራሳቸው መሬት ላይ እንደ ማይኖሪቲ መታየታቸው የብሄር ጭቆና አይደለም ወይ? “አናሳው” ብዙሃኑን የሚጨቁንበት ስርዓት ተፈጠረ ማለት ነው። ለዚህ ነው የብሄር ፖለቲካ በሁለት አቅጣጫ የተሳለ ሰይፍ አለው የሚያስብለን። በአንድ በኩል አብላጫ ቁጥር ያለው ስልጣን ሲይዝ የማጆሪቲ አምባገነን ሲፈጠር፣ ማይኖሪቲ የበላይ ሲሆን ደግሞ የማይኖሪቲ አምባገነንነትን ስለሚያመጣ ከብሄር ጭቆና ነጻ አያወጣም። ጨቋኝ የነበረውን ተጨቋኝ፣ ተጨቋኝ የነበረውን ጨቋኝ እያደረጉ በበቀል ጎዳና ከመነዳት ይልቅ ለምን ከዚህ አንወጣም?

 

የፓለቲካ መብትን በሚመለከት የሃረሪን ጉዳይ ስናይ ከፍተኛውን ስልጣን የክልሉ ተወላጆች ሲይዙ ኦሮሞዎችም የክልሉ ተወላጆች ሆነው ሳለ ሁል ጊዜ ሊቀመንበሩ የሃረሪ ሰው እንዲሆን መወሰኑ ምክትሉ የኦሮሞ እንዲሆን መወሰኑ ደግሞ ይገርማል። ሊቀመንበር በመሆን ነው የክልል ባለቤትነት የሚረጋገጠው ማለት ነው? ጋምቤላ ውስጥ እንዴት ነው ሊቀ መንበር የሚኮነው? ቤንሻንጉል ደቡብ  ወዘተ. ይህ አካሄድ ምንም መሰረት የሌለው የእንዳወጣው የግብር ይውጣ ስራ ይመስላል። የብሄር ጭቆናን  በግልጽ የሚያራምድ ስራ እየተሰራ ያለበት ሁኔታ ላይ ነው ያለው። ይህ ክልል ሲቋቋም በፈቃድ ላይ ስለተመሰረተም አይደለም። የሃረር ህዝብ የታወቀ ነው። የሃረርና የድሬ ህዝብ በእንግዳ ተቀባይነቱ፣ ከሁሉ ጋር በመኖር ችሎታው መላው የኢትዮያ ህዝብ ይመሰክርለታል። ውድ ህዝብ ነው በጣም። እንዲህ አይነት ዘረኝነት ሲያይ አቦ ይሄን ዘረኝነት ወደዚያ ውሰዱልን ነው የሚለው። ተግባሩ ራሱ የሃረርን ህዝብ ባህል ያላገናዘበ የሃረርን ህዝብ እሴቶች የጣሰ ነው።

 

ሃረር ውስጥ ከዘጠና አንድ በመቶ በላይ የሆነው ህዝብ እየታዘበ የክልሉ ርእሰ መስተዳድር ከሃረሪ ተወላጅ ብቻ ነው ሁለተኛው ከኦሮሞ ነው የሚለው ህግ ከየት ነው የሚመጣው?  የ“ማይኖሪቲ” ሩል አሰራርን በማምጣትና የብዙሃኑን የፖለቲካ ተሳትፎ በመገደብ ፍትህ ተበየነ ማለት ነው ወይ? በሌላ በኩል ያለው አስገራሚ ጥያቄ ደግሞ እነዚህ “መጤ”  የሚባሉት በየክልሉ ያሉ ኢትዮጵያውያን በአሜሪካንና በአንዳንድ አገሮች እንደሚባለው ህገ-ወጥ መጤዎች (Illegal immigrants or undocumented immigrants) መሆናቸው ይሆን? ይገርማል መቼም:: እነዚህ ስደተኞች አንዳንዶቹ በ18ኛው ክፍለ ዘመን አያቶቻቸው ወደዚያ  የሄዱ ናቸው። እነዚህ የልጅ ልጆች መቼ ነው በክልሉ መንግስት የክልል ዜግነት ወይም ሌላ ዶክመንት ካለ ተሰጥተው ሙሉ የፖለቲካ ተሳትፎ የሚኖራቸውና የክልሉ ተወላጆች ወይም የክልል ዜግነት ካለ የክልሉ ዜጎች የሚባሉት? በክልሉ ውስጥ የተወለዱት የክልሉ ተወላጅ ስለምን አይባሉም? አንድ ህዝብ በአንድ መሬት ላይ ሌላው ይቅርና የመቶ አመት  እድሜ ካለው  በቃ አገሩ እኮ ነው። የዚያ ዜጋ የዚያ ሃገር ባለቤት ይሆናል። ፈልሳችሁ ነው የሚባል ነገር ከሰው ልጆች ታሪክ ጋር አይሄድም።  ኢትዮጵያ ራሷ የተፈጠረችው በኦሮሞ መስፋፋት፣ በአማራ መስፋፋት፣  በደቡብ ህዝቦች መስፋፋት በሁሉም ህዝቦች ንቅናቄ ነው። የጊዜው ርዝማኔ ይለያይ እንጂ ሁሉም ብሄሮች ከዚህ ነው የመጣነው፣ ከዚያ አገር ነው የመጣነው የሚል አፈ ታሪክና የተጻፈ ታሪክ ይኖራቸዋል። መሬትን በእጁ ጠፍጥፎ የሰራ የለምና ሰዎች ተነቃንቀው ለረጅም ጊዜ ከኖሩ በኋላ በዚህ በሰለጠነው ዓለም ጊዜ እንዲህ ዓይነት አሰራር ማምጣት በዓለም አልታየም። በተለይ በተለይ አንድ ሰው የተወለደበት አገር አገሩ መሆን አለበት። ያ የተወለደበት አገር አገሩ የማይሆንበት ምንም ምክንያት የለም። ተወልዶ ያደገበትን ምድር የመንከባከብ የመግዛት ችሎታ አለው። ይሄ ግልጽ ሎጂክ ነው። በአሜሪካ ህግ አንድ ሰው በአሜሪካ የአየር ክልል ውስጥ በአውሮፕላን ሲሄድ ቢወለድም እንኳን ዜግነት የማግኘት መብት አለው። አሜሪካ አገሩ፣ የዚህ ዓለም እጣ ፈንታው ትሆናለች። ይሄ ትክክለኛ ጥርት ያለ ሎጂክ ነው። የኢትዮጵያ ፌደራሊዝም ግን ይህን የዴሞክራሲ  መብት አፈር አብልቶታል።

 

ሌላው መሳጭ ጉዳይ ደግሞ የቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ጉዳይ ነው። ቤንሻንጉል ጉሙዝ እንደ ክልል የተፈጠረው ከቀድሞው ምእራብ ጎጃም እና ከሰሜን ምስራቅ ወለጋ ክፍለ ሃገራት ነው። ይህ ክልል በሶስት ዞኖችና በሃያ አንድ ወረዳዎች የተዋቀረ ሲሆን 50,699  ስኩየር ኪሎ ሜትር የቆዳ ስፋት አለው። 784,345 ህዝብ ይዟል። የህዝብ ብዛት ደንሲቲው ደግሞ 15/Km2  ያህል ነው። በዚህ ክልል ውስጥ ብዙ ቡድኖች የሚኖሩበት ሲሆን ከአጠቃላይ ህዝቡ ውስጥ 25.41% በርታ፣  21.69% አማራ፣  20.88% ጉሙዝ፣  17.69% ኦሮሞ  7.73% ሺናሻ  4.01%  አውንጊ፣ ናቸው። ይሁን እንጂ ይህ ክልል በዋናነት በባለቤትነት የተሰጠው ለበርታና ለጉሙዝ ነው። ሌሎቹ በተለይም ኦሮሞና አማራ እንደ መጤ እንዲታዩ ይደረጋል። ስያሜውን ስናይ በሁለቱ ስም ነው የሚጠራው። ደቡብ ውስጥ ብዙ ስለሆኑ የደቡብ ብሄር ብሄረሰብና ህዝቦች እንደተባለው ሁሉ ካንድ በላይ ብሄር ያላቸውን በሆነ ስያሜ አስገብቶ የጋራ መሆኑ እዘህ ክልል ላይ ደግሞ አይሰራም። ለመሆኑ ግን ይህ ክልል የተወላጁ ነው ስንል ምን መረጃ ይዘን እንደሆነ ባይታወቅም እዚህ ቤንሻንጉል ውስጥ በተለይም ሁለቱ ዋና ባለቤቶች ማለትም ጉሙዝና በርታ ዴሞክራሲን ለማስተናገድ ሲሞክሩ የማጆሪቲ ሩልን ጉዳይ የግድ ከቡድኑ ብዛት ጋር ሊያያይዙ ነው ማለት ነው። ሃረር ውስጥ ማይኖሪቲው በመጤው ላይ የፖለቲካ የበላይነት እንዲኖረው ሲደረግ ቤንሻንጉል ደግሞ አቶ መለስ ራሳቸው በፈጠሩት ክልል “ከዋናዎቹ” ብሄሮች ብዛት ያለው የበላይነቱን ይዞ ይኖራል ማለት ነው። በዚህ የብሄሮች ፍትህ ተበየነ ማለት ነው?

 

አንድ ክልል ጋምቤላም ይሁን፣ ኦሮምያ ወይም ሌላ ክልል ይህ ክልል የተወላጆቹ ነው ከተባለ ኢትዮጵያዊነት የማይጨበጥ አሳብ ብቻ ይሆናል ማለት ነው። ኢትዮጵያዊነት መሬት የለውም ማለት ነው። ዜግነት መሬት የለውም። ይህ ግዙፍ ሃብት በዚህ በብሄር ፖለቲካና በብሄር ፌደራሊዝም ጊዜ ዋጋ ያጣል።  ኢትዮጵያዊነት ማለት በኢትዮጵያዊነት በዜግነት ከኢትዮጵያ የምናገኘው የፖለቲካና የመሬት ባለቤትነትን የሚያሳይ ነው። ዜጎች በሄዱበት ቦታ በአራቱም ማእዘናት የመኖር የመስራት በሃገራቸው ፖለቲካ ላይ የመሳተፍ መብት አላቸው። ይህ መብት የሚዘረዘረው በኢትዮጵያዊነት በዜግነት መብት መከበር በሚጀምርበት ጊዜ  ነው። ቤንሻንጉል ጉምዝ ውስጥ ተደምረው ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ኢትዮጵያውያን የፖለቲካ ተሳትፎአቸው ይገደባል። ምክንያቱ ደግሞ የዛሬ መቶ ሁለት መቶ አመት ሊሆን ይችላል አባትህ ከኦሮሞ ወይም ከአማራ ወይም ከደቡብ አለያም ከትግሬ መጣ በማለት ነው። ይሄ በዓለም ያልታየ ታሪክ ይመስለኛል። ከፍ ሲል እንዳልነው ዓለም በንቅናቄ ነው የተፈጠረችው። የትም አለም የሰው ልጆች ተነቃንቀዋል። አሁን በዚህ ዘመን ነው አንጻራዊ ርጋታ ያለው። ያም ሆኖ ግን እስካሁን በዓለም ላይ ወደ 200 አገራት የድንበር ክለላ ጣጣ ያልጨረሱና በተለያየ ደረጃ ግጭቶች ያሉባቸው ናቸው።

 

ከተባበረችው አሜሪካ ብዙ ልንማር የሚገባ ይመስለኛል። አንድ የማውቀው ሰው እድሜው ከሰላሳ በላይ የሆነ ዲቪ ደርሶት ሄደ። በዚያ ጥቂት አመታት ቆይቶ እነሆ ዛሬ ዜጋ ነው። የወለዳቸው ልጆችና እሱ በስተርጅና ያገኘው ዜግነት ሙሉ ፓለቲካዊና ማህበራዊ መብትን ሰጥቶታል። በቃ አሜሪካ ውስጥ የፈለገበት ስቴት ሄዶ ቢኖር መብቱ አይሸራረፍም። በእንዲህ አይነት አለም ላይ እየኖርን ቅም አያቱ ከጎንደር የመጡ ናቸውና ቤንሻንጉል የሱ ክልል አይደለም የሚባል ነገር አይሰራም። ጎንደር በሃገሩ የመንቀሳቀስ መብት አለውና።

 

በዓጼ ምኒሊክ ዘመን ዓለም በንቅናቄ ላይ ነበረች። የተሰሩ በደሎች የሉም አይደለም። በሚገባ አሉ። በጦርነት የተጎዱ፣ የተፈናቀሉ ብዙ በደሎች አሉ። ዓለም እንደሆነ ሆነናል። ይህን ታሪክ የምናድሰው የዛሬ አምሳ አመት መቶ አመት መፈናቀል ነበር ብለን ከዚያ እኛው ክልል ፈጥረን አንተ ከዚህ ክልል ፈልሰሃል ይሄ ክልል  የእንትናና የእንትና ብቻ ነው ለማለት ምን ችሎታ አለን? ለምን  ለሁሉም የሚሆን ሁሉን ነጻ የሚያወጣ መፍትሄ አናመጣም።  ራሳችን እንዳሻን ክልል ፈጥረን ሰዎችን ማፈናቀል የለብንም። ኢትዮጵያ ስትፈጠር ዘጠኝ ክልል ነበረች የሚል ታሪክ የለም። ይህን ዘጠኝ ክልል የፈጠሩት አቶ መለስ ናቸው። እሳቸው በፈጠሩት ክልል ውስጥ እከሌ መጤ እከሌ ነባር ለማለት ችሎታው የላቸውም። አቶ መለስ ኢትዮጵያን በዘጠኝ ከከፈሉ በሁዋላ የደቡብ ብሄሮች የክልልነት ጥያቄ ሲያቀርቡ ክልል አለቀ አሁን ወደ ልማት ነው ብለው መለሷቸው።

 

ቤንሻጉል ውስጥ ያሉ ሁሉቱ ገናና ቡድኖች ማለትም በርታና ጉሙዝን የፖለቲካ ሽኩቻ ውስጥ የከተታቸው የፖለቲካው አባዜ ነው። ጉምዞች በርታ ተጭኖናል የሚሉት በቁጥሩ ስለበዛና ማጆሪቲውን ስለያዘው ነው። ጉምዞች እልህ ውስጥ ከገቡና ማጆሪቲ መሆን ካማራቸው ምንድን ነው መፍትሄው? ቶሎ ቶሎ መዋለድ ነው ማለት ነው። ለምን ወገኖቻችን የፖለቲካን ጥበብ ከዚህ ከዚህ ጋር እንዲያያይዙ እናደርጋለን። ለምን ፍትህን  መርህን እንዲመረኮዙ አናደርግም የሚለው ጥያቄ ዛሬስ በመረረ ሁኔታ መነሳት አለበት።

 

ጋምቤላም ብንሄድ እንደዚሁ ነው። ጋምቤላ ውስጥ ወደ አምስት የሚሆኑ ብሄሮች የጋምቤላ ክልል ባለቤቶች ናቸው ይባላል።  ከነዚህ ውጭ ያሉት ቡድኖች መጤዎች (illegal immigrants) ናቸው። ከፍ ሲል እንዳልነው ላለፈው መቶ አመት በላይ ህገ ወጥ ሆነው የኖሩ ናቸው ማለት ነው። ጋምቤላን በባለቤትነት ከሚያስተዳድሩ አምስት ዋናዋና ብሄሮች መካከል ሁለቱ ማለትም የኑየር ብሄርና የአኙዋክ ብሄር መካከል የሚታይ የሃይል ሽኩቻ የመነጨው ከዚያው ከብሄር ፖለቲካ ነው። አንድ ነገር ልብ ማለት ያለብን እነዚህ ቡድኖችም ይሁኑ በየትኛውም የሃገሪቱ ክፍል የሚነሱ የብሄር ግጭቶች ቡድኖች አብረው ለመኖር ካለመፈለግ ወይም አብሮ መኖር እንግዳ ስለሆነባቸው አይደለም። እንግዳ ሆኖ የሚያጋጫቸው የጎሳ ፖለቲካና በውስጡ የያዘው እምቅ ግጭቶች ናቸው። ከዚያ በተረፈ የቤንሻንጉል ጉሙዝ፣ የጋምቤላ፣ የሃረሪ፣ የደቡብ፣ የአማራ ወዘተ ከሌሎች ኢትዮጵያውያን ጋር በመኖር አይጋጩም። ኢትዮጵያዊ ሁሉ ደግየ ህዝብ ነው።

ብሄር ተኮር ግጭቶች በዚህ ዘመን በጣም ከፍ ያሉ ሲሆን አብዛኛው በመንግስት በምስጢር ስለሚያዝ መረጀ ይጠፋል እንጂ ከፍተኛ የሆነ የብሄር ፖለቲካ የወለደው ፌደራሊዝም ብዙዎችን አሳጥቶናል ሰላም ነስቶናል።

 

ግን ግን…..ከሰባዊ መብት አኳያስ እነዚህ ሰዎች የት ይሂዱ? እስከ መቼስ ነው የክልሉ ተወላጅ የሚባባሉት የሚለው ጥያቄ ትልቅ የሰብአዊ መብት ጥያቄ ነው።ሌላው ይሄ የብሄር ፓለቲካ የወለደው የብሄር ፌደራሊዝም በዜጎች የሃገር ባለቤትነት ላይ ችግር ሲፈጥር የዚህ ችግር ዋና ተጋላጭ የሆነው ማህበረሰብ ከሁለትና በላይ ብሄሮች የተወለደው ቅይጡ ኢትዮጵያዊ ነው። ይህ ዜጋ በህወሃት ጊዜ የተሰጠው እድል ወይ እናቱን ወይ አባቱን እንዲመርጥ ነው። ይሄ ደግሞ ሳይንስ የጎደለው ተራ ነገር ነው በውነት። አንድን ዜጋ ከናትህና ከአባትህ ምረጥና የአንድ ብሄር አባል ሁን ሲባል ይህ ሰው ሁለቱንም ይወዳል። ከሁለቱም የወራሽነት ሙሉ መብት አለው። ሁለቱንም ማስከፋት አይፈልግም። የሚገርመው ይህ ህዝብ በቁጥሩ ደግሞ ከኦሮሞና አማራ ቀጥሎ የሚሰለፍ ነው።ግዙፍ ህዝብ ነው ለዴሞክራሰያዊ መብት ድርቅ የተጋለጠው። በአንድ የደቡብ ክልል ውስጥ ያየሁት ነገር እስካሁን ይገርመኛል። የወረዳው ምክር ቤት ጸሃፊ ከሁለት የተለያዩ ብሄሮች የተወለደ ነው። ይህ ሰው አንዱን መርጦ የመጣ ነው ማለት ነው። የሚገርመው ይህን ስልጣን ይያዝ እንጂ ተሰሚነቱ ግን ዝቅ ያለ ነበር። እሱ የወሰነውን የሴክተር ሃላፊው ይሽረዋል። እሱም ይህን ተረድቶ በዘያው በግማሽ መብቱ ይኖራል። ጎበዝ ቢሆንም ተሰሚነቱ ግን በዚህ በዘሩ ምክንያት ቀንሷል። የዚህን ባለስልጣን ምሳሌ ሳነሳ ከኦሮሞና አማራ የተወለዱት፣ ከጉራጌና ወላይታ የተወልዱት ወዘተ በአጋጣሚ ወደ ስልጣን ሲመጡ ባሉባቸው ክልሎች ተሰሚነታቸው እንደ ሌሎቹ የብሄሩ አባላት አለመሆኑን ማሳያ ስለሚሆን ነው። ሌላው አስገራሚ ነገር ደግሞ በዚያ ወረዳ ውስጥ ያሉ በተለይ የሰሜን ተወላጆች ያንን የሃገራቸውን ክፍል በፓለቲካ ተሳትፎ የማገልገል አሳቡም የላቸውም። የሚያስጠጋቸው የለምና። የኢትዮጵያ የፓለቲካ መብት ወንዝ አትሻገርም። በዚህ ወረዳ ይኖሩ የነበሩ የሌላ ክልል ዜጎች እንደ ውጭ ዜጋ ይታያሉ። ህዝቡ ነው እንጂ ጥሩው አስተዳደሩ ባይተዋር ያደርጋል። በዚያ ወረዳ ውስጥ በተለይ ከመሃል አገር የመጡ የጤና ባለሙያዎች የግብርና ሰራተኞችና አስተማሪዎች ራሳቸውን የሚያዩት ልክ የአእምሮ ሃብታቸውን ሸጠው የግል ህይወታቸውን ለመምራት የመጡበት ክልል እንጅ የእናት አገር ስሜት እንዳያዳብሩ የተደረጉ ይመስላሉ።

 

ሌላው በዚህ የፌደራል ስርአት ለዴሞክራሰያዊ መብቶች እጥረት የተጋለጠው የህብረተሰብ ክፍል ደግሞ ብሄሩን በትክክል የማያውቅና የየትኛውም ብሄር አባል ነኝ ሲል ምቾት የማይሰማው ዜጋ ነው። ይህም በቁጥሩ ቀላል አይደለም። ይህን ሁሉ ህዝብ እየጎዳ ያለ ስርአት ነው።

 

 

አስተዳደራዊ አመቺነትና እድገት

 

በሌላ በኩል የኢትዮጵያ የፌደራል አወቃቀር ለማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እድገት አይጠቅምም። አስተዳደራዊ አመቺነት በክልል ምስረታው ወቅት ቦታ ስላልነበረው ተያይዞ ለማደግ የሚመች አይደለም። ከክልል ቅንጅት የክልል ግጭት ሊያይል ይችላል። ያለንን ውሱን የተማረ ሃይል በቅጡ እንዳንጠቀም ያደርጋል። ይሄ ደግሞ ትልቅ ሁለንተናዊ የሆነ ችግርን ያመጣል። በእውቀት ላይ ተመስርተው ሊሰሩ የሚገባቸው ጉዳዮች ሳይሰሩ ይቀራሉ፣ የሃገር ሃብት ያለ ብልሃት ይባክናልና በኢኮኖሚ እድገታችን ዙሪያ አሉታዊ ተጽእኖ ይኖረዋል። በአንዳንድ ከፍተኛ የልማት ስራዎች ላይ ፌደራል መንግስት በአንዳንድ ክልሎች ሊሰራ በሚያስባቸው ፕሮጀክቶች ላይ ከአራቱም አቅጣጫ የሚገኘው ድጋፍ አመርቂ አይሆንም።

 

በክልሎች መካከል ያለው ዲሞግራፊና ደንሲቲ እጅግ የተራራቀ በመሆኑ ያለንን የተፈጥሮ ሃብት ፍትሓዊ በሆነ መንገድ እንዳንጠቀም ስለሚያደርግ የኢኮኖሚ እድገታችንን ይገታዋል። የኢትዮጵያ የድህነት ችግር ማህበራዊ ችግር በመሆኑ ከፍተኛ የሆነ የኮሚኒቲ ልማት ስራዎችን መስራት ያስፈልጋል። ለዚህ ደግሞ ጠንካራ የቅስቀሳ ስራና የብሄራዊነት ስሜት ያሻል። ከሰማኒያ በላይ የሚሆኑ ባህላዊ ቡድኖችን እንዳወጣው በዘጠኝ ከፍሎ ደግሞ በላዩ ላይ የብሄር ፖለቲካን ቸልሶ መኖር ልማትን አያፋጥንም። ከፍ ሲል ያልነውን ምሳሌ ማንሳት በቂ ነው። በሃረሪ ውስጥ የሚኖሩ ከዘጠና አንድ በመቶ የሚበልጡ ኢትዮጵያውያን መጤዎች ከሆኑ እንዴት ብለው ነው ለዘላቂና ለልጅ ልጅ የሚሆን ስራ ለመስራት የሚፈልጉት። ጋምቤላ፣ ቤንሻንጉል፣ አፋር፣ ኦሮሚያና ሌሎችም ክልሎች ውስጥ ያሉ መጤ የተባሉ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ኢትዮጵያውያን ሃብት ለማፍራትና የመጨረሻ ሃይላቸውን አሟጠው በኮሚኒቲ ልማት ስራ ላይ ለመሳተፍ አያስችላቸውም። አካባቢን ለመቀየር አዋጅ ያስፈልጋል። ለአካባቢ ለውጥ ትልቅ የኮሙኒቲ ንቅናቄ (Community mobilization) ስራም ያስፈልጋል። እነዚህ ጉዳዮች ደግሞ ሃይል የሚሆናቸው ብሄራዊ ስሜት ሲገንን ነው። ምንም የማያስገኝ፣ መሬት እንኳን የሌለውን ኢትዮጵያዊነት ይዘው ሃይላቸውን አሟጠው ዜጎች አይሰሩም።

 

በሌላ በኩል ፌደራሊዝሙ ለዜጎች ፍትህን ለማገልገል ችግር ሆኖ ያታያል። አንድ የመርሃ ቤቴ ሰው ወደ ክልል የሚያደርስ የፍትህ  ጉዳይ ወይም የአገልግሎት ጉዳይ ቢገጥመው አዲስ አበባን አቋርጦ ረጅም ጉዞ ተጉዞ ነው ባህዳር የሚመጣው። ደቡብና ኦሮሚያ  አንዳንድ ቦታዎችም ላይ ይሄ ችግር አለ። ቅርባቸው ያለውን አዋሳን ጥለው ናዝሬት ድረስ መሄድ ያለባቸው ኦሮሞዎች አሉ። የኦሮሚያ አቀማመጥ ግዙፍ በመሆኑ ለዜጎች አስቸጋሪ ነው። ከአንፊሎ ምእራብ ወለጋ እስከ አዳማ ድረስ ምን ያህል ይርቃል። ከቦረና ተልተሌ ተንስቶ ስንት አገር አቋርጦ አዳማ ለመድረስ ምን ያህል ገንዘብ ይፈጃል፣ ምን ያህል ያደክማል። የፌደራል ስርዓት አንዱ ትልቁ ጥቅሙ ስልጣንን በማውረድ ለዜጎች ፍትህን ማደል ነው። ኦሮሚያ አንድ ክልል ሆኖ የሃገሪቱን አንድ ሶስተኛ መሬት ይዞ ይገኛል። አንድ የሃረሪ ሰው ደግሞ ክልል ቢሮ ለመሄድ በእግሩ ትንሽ ሰዓት ብቻ ይፈጅበታል። አማራ ክልል ውስጥ ያሉ የመርሃ ቤቴና የመንዝ አስተዳዳሪዎች ለስራና ስብሰባ ባህርዳር የውሃ መንገድ ናት። ወጪው ስንት ነው? ……………….ውጥንቅጡ የወጣ የፌደራል ስርአት።

 

ማጠቃለሊያ

እውነቱን ለመናገር የኢትዮጵያን የፌደራል ስርአት መግለፅ ይከብዳል። ክልል አፈጣጠሩ አንድ ትግራይን በኢኮኖሚ የተሻለች ለማድረግ የተጨነቀ ብቻ ይመስላል። አልፎ አልፎም ተንኮሎችም ያሉት ይመስላል። ለምሳሌ ያህል በአማራ ክልል የኦሮምያ ዞን የሚባል አለ። ወልቃይት ግን በትግራይ ክልል የአማራ ዞን አልተባለም።  ህወሃት ይህንን የኔ የሚለውን ክልል ለመጥቀም ሲል በሃገሪቱ ፓለቲካ ውስጥ ልዩነትን፣ ምስለትን፣ የብሄር ፓለቲካን  የግለሰብ መብት መደምሰሰን በአንድ ጊዜ በአንድ ዘመን እንዲፈፀሙ አድርጓል። ትግራይ ላይ የተጨነቀውን ያህል ለሌሎች ክልሎች ደንታ የለውም። የዚህ ችግር ክፋቱ ተፅእኖው ከባድ መሆኑ ነው። የሃገሪቱን ህልውና ሳይቀር አደጋ ላይ የጣለ ነው።

 

አሁን ያለው የፌደራል ስርአት የፌደራል ስርአት አይባልም ምክንያቱም የፌደራል ስርአት ባህርያት የሉትም ብለናል። እንዲህ ሲባል ታዲያ ምን አይነት ስርአት እየተከተልን ነው ስርአቱ በምን ይገለፃል የሚል ጥያቄ ይነሳል። ከፍ ሲል እንደተገለፀው ስርአቱን በሚገባ ለመግለጽ ቢከብድም ከስልጣን ባህርዩ አንፃር ይገለፅ ከተባለ አሃዳዊ አምባገነን አይነት ሲሆን ጎጠኛ ኦሊጋርኬም ነው። ኢትዮጵያ የፌደራል ስርአትን ከነ ሙሉ ክብሩ ልትጠቀም የቻለች አገር አይደለችም። ያሳዝናል። ብዙህ በሆኑ ሃገራት ውስጥ ፌደፍራሊዝም የሚመረጥበት አንዱ ዋና ነገር ግጭትን ቀንሶ ሰላምን ለማስፈን ነበር። በኢትዮጵያ ውስጥ ይህ የፌደራል ስርአት ከተጀመረ ወዲህ የብሄር ግጭቶች ከመቼውም ጊዜ የበለጠ ይታያል። ይህ የሆነበት ምክንያት እውነተኛ ፌደራሊዝም ስለሌለ ነው። ስልጣን በሃይል ስለተማከለና ስልጣኑ ደግሞ ጎጥን መከታ ስላደረገ ነው።

 

በርግጥ ለአዲሲቱ ኢትዮጵያችን ተመራጭ የሚሆነው ስርአት የፌደራል ስርአት ነው። ይህ የፌደራል ስርአት ታዲያ ማንነቶችን ማለትም ብሄራዊ ማንነትንና ባህላዊ ማንነትን አጣጥሞ የሚሄድ መሄን አለበት። ለአስተዳደር አመቺ፣ ለጋራ እድገት አመቺ መሆን አለበት። እንዳንድ ወገኖች ፌደራሊዝም ካሉት ችግሮች አንዱ ብሄራዊ ስሜት እየጎዳ አካባቢያዊ ስሜትን ያሳድጋል የሚል ነው። አይመስለኝም። በርግጥ ይህ ችግር ሊከሰት የሚችለው ክልሉ ብሄርን ብቻ መሰረት ካደረገና የብሄር ፓለቲካ ካለ ነው። ሰኪዩላር በሆነ የፌደራል ስርአት ውስጥ ይህ ችግር አይከሰትም። እንዴውም ዜጎች ፓለቲካዊ በሆነ መንገድ በእለት ከእለት ኑሯቸው ሁለት መንግስታትን አያሰቡ የሚኖሩ አይመስለኝም። ለምሳሌ አሜሪካ ወይም አውስትሬሊያ ወይም ካናዳውያን የትም ስቴት ቢሄዱ ባይተዋርነት አይሰማቸውም። የእኔ ባለቤት አሜሪካዊት ስትሆን በምንም አይነት ፓለቲካዊ የሆነ የብሄራዊና የአካባቢያዊ ማንነት ሽሚያ አላይባትም። ያደገችበትን ቀየ እንደማንም ሰው ስትናፍቅ ከማየቴ ውጭ ብሄራዊ ማንነቷና የክልል ስሜቷ ሳይጋጩ አድጋለች።  በአንፃሩ እኔ ብሄራዊ ማንነቴን ከክልላዊ ማንነቴ ጋር እንዳይጋጭ ስታገል አገኘዋለሁ። ወያኔ የፈጠረውን የብሄር ፌደራሊዝም እምቢ እያልኩ ፓለቲካዊና ባህላዊ ማንነቴን በተለያየ ሲስተም ለማሳደር አሳብ ለማፍለቅ እታገላለሁ።

 

በመሰረቱ ፌደራሊዝምን ወደ ኢትዮጵያ ልናመጣ ስናስብ እኛ ኢትዮጵያውያን መጠንቀቅ ያለብን የምንዘረዝረው መንግስት የብሄራዊ መንግስት ክፋይ መሆን የሚኖርበት ሲሆን ፌደራሊዝሙን የባህል ቡድነኝነት መከለያ ካደረግነው ብዙ እምቅ ግጭቶችን ያመጣብናል። በመሆኑም የሚሻለው ሁለት አይነት የፌደራል ስርአት መፍጠር ነው። አንዱ የባህል ፌደሬሽን ሲሄን ይህም ባህልን የሚንከባከብ ሃሳባዊ የፌደራል ስርአት ሲሆን ሌላው ለአስተዳደር፣ለዴሞክራሲ ለልማት ምቹ የሆነ የፌደራል ስርአት እንደገና ማዋቀር ነው። ፓለቲካችንን ከማንነት ፓለቲካ አፅድተን ሳይንሳዊ ፌደራል ስርአት መዘርጋት እንችላለን። ባህላችንን በባህል ፌደሬሽን መካደም ይቻላል። ይህ አሰራር ለኢኮኖሚ እድገትም ከፍተኛ አስተዋፃ አለው።

 

ለዚህ ሁሉ ግን አገራችን ወደ አዲስ የቡድኖች ኪዳን መግባት ይኖርባታል። ይህ የቡድኖች ኪዳን የኢትዮጵያን ማህበረ ፓለቲካ እስተካክሎ ይሰራልናል። ኢትዮጵያ አዲስ ኪዳን ትገባ ዘንድ ኢትዮጵያዊ ሁሉ ሊነሳ ይገባል። ስለዚህ አዲስ ኪዳን ስለምለው ጉዳይ ሌሎች ፅሁፎችን እፅፋለሁ። ለዛሬ በዚሁ ላብቃ።

 

እግዚአብሄር ኢትዮጵያን ይባርክ

አስተያየት ጥሩ ነው

geletawzeleke@gmail.com

 

 

 

 

 

 

 

 


ዋናው የሰልፉ ዓላማ በሌላ ‹‹የተቀደሰ ዓላማ›› እንዳይዳፈን ስጋት አለ –ሙሉቀን ተስፋው

$
0
0

ጎንደር በፌደራልና በልዩ ኃይል ፖሊሶች ተጨናንቃለች

welkeit - satenaw

ሐምሌ 24 ቀን 2008 ዓ.ም. በጎንደር ከተማ ከግማሽ ሚሊዮን የሚልቁ ዐማሮች ሰላማዊ ሰልፍ ይወጣሉ፡፡ ይህን ተከትሎ ከባሕር ዳር፣ ደብረ ታቦር፣ ደባርቅ፣ ቆላ ድባ፣ ሳንጃና ጭልጋ መተማ የሚመጡ መኪኖች ላይ ታላቅ ፍተሸ እየተካሔደ ነው፡፡ ከጭልጋ ሰራባ አካባቢ እንዲሁም ከባሕር ዳር ብዛት ያላቸው የመከላከያ ኃይል አባላት ወደ ጎንደር መጥተዋል፡፡ በጎንደር የሚታየው ፖሊስ ዛሬ በጽጥታ አካላት ብቻ ሰልፍ የተካሔደ አስመስሎታል፡፡

ዐማሮች ከሁሉም ቦታ ወደ ጎንደር እየጎረፉ ነው፡፡ የሰልፉ ዓላማም አንድ እና አንድ ነው፤ ይኸውም የወልቃይት ዐማሮች የማንነት ጥያቄን ለማዳፈን የሚደረገውን ጥረት መቃወም ነው፡፡ ኮሚቴዎች በአስቸኳይ ያለምንም ቅድመ ሁኔታ እንዲፈቱ መጠየቅ፤ ወልቃይት ዐማራነትን መመስከር ነው፡፡
ይህ ሰልፍ ከዚህ የዘለለ ሌላ ዓላማ የለውም፡፡ ሆኖም ይህን ሰልፍ ዓላማ በሌላ ‹‹የተቀደሰ ዓላማ›› ለመሸፍ የሚደረግ ጥረት አለ፡፡ የኦሮሞ ወንድሞቻችን ግድያና አፈና፣ የሀብታሙ ሕመም ሁላችንም የምናወግዘው ጉዳይ ነው፡፡ የኢትዮጵያን መበታተን ማንም አይሻም፡፡

እነዚህ ‹‹ቅዱስ ዓላማ›› ያላቸው መፈክሮች ጎልተው የሰፊውን ዐማራ ሕዝብ ጥያቄ በማወቅም ይሁን ባለማወቅ ለማዳፈን የሚደረገው ጥረት ዋጋ ያስከፍላል፡፡ ስለዚህ የዐማራውን ሕዝብ ትግል እንቅስቃሴ በሕዝቡ ላይ የሚደርሰውን በደል በማጋለጥ ላይ ብቻ ያተኮረ ነው፡፡ ሁሉም የሰልፉ ተሳታፊ የዐማራ ሕዝብ ከወልቃይት ጠገዴ የዐማራ የማንነት ጥያቄን በደንብ አጉልቶ ማውጣት አለበት፡፡

 

Health: ስለኩላሊት ጠጠር ማወቅ ያለብዎ ቁምነገሮች

በጎንደር የአማራ ልዩ ኃይልና የአካባቢ ሚሊሻ ህዝባዊነት እያሳዩ ነዉ ተባለ

$
0
0

File Ethiopia

File Photo


ከልዑል ዓለሜ

በጎንደር ተሰማርቶ የሚገኘዉ የመከላከያ ሰራዊት አባላት የልዩ ሐይልና የአካባቢ ሚሊሻ ባጠቃላይ ነገ የሚካሄደዉን የጎንደርን ሰልፍ ተነተርሶ የተሰጣቸዉን ሰላማዊ ሰልፍ የማክሸፍ ሴራ ያለማቀበላቸዉን የሚጠቁሙ መረጃዎች ደርሰዉናል።
· ከየትኛዉም መንደሮች ወደ መሰብሰቢያ ቦታዉ የሚወስዱ መንገዶች በጸጥታ ሐይሎች እንዲዘጉ።
· ሰልፉን ያስተባብራሉ ይመራሉ ይቀሰቅሳሉ የሚባሉ ግለሰቦች ከድርጊታቸዉ እንዲታቀቡ ማድረግ…… (ይህ ሁኔታ የጸጥታ ሐይሎችን በመጠቀም ማስገደድንም ይጭምራል)
· የስረርቱን ቀንደኛ ደጋፊ ብአዴኖችን በመጠቀም ጥቆማዎችን አይነተኛ መሳሪያ አድርጎ ማባበያ (መደለያ) እና ማዘናጊያ እቅዶችን ማስፈጸም!!
· ይህ ካልሆነ በጸጥታ ሐይሎች ተጠቅሞ እርምጃዎችን በተጠና ሁኔታ መዉሰድ>>>> የሚሉ ሲሆኑ እነዚህና የመሳሰሉት ሂደቶች ዉጤታማ ስይሆኑ ቢቀሩና ሰልፉ ቢካሄድ የመከላከያ ሰራዊቱ ዝግጁ እንዲሁን ትእዝዝ ቢተላለፍም ባጠቃላይ የመከላከያ ሰራዊት አባላትና የጸጥታ ሐይሎች ብሎም የአካባቢ ሚሊሻ . . . . . ” አንዳችም ሰዉ ላይ ጉዳት አናደርስም ” አፈና አናካሄድም! ህዝቡ መብቱን በሰላማዊ መንገድ እየገለጸ ከመካከላችን አንዳች ስህተት ቢሰራ ዝም ብለን አንመለከትም! በማለት አቋማቸዉን የገለጹ ሲሆን በተለይም የአካባቢ ሚሊሻዎች በተለየ ሁኔታ ከህዝቡ ጎን መቆማቸዉን በድፍረት ተናግረዋል።

እነዚህ ሁኔታዎች ሁሉ ገደል በገደል የሆኑበት የትግራዩ ነጻ አዉጪ ቡድን ሰሜን ጎንደር አይከል አካባቢ ያሰፈረዉን የአጋዚ ጦር ወደ ጎንደር እያስገባ ከመሆኑ በተጨማሪ በባሕር ዳር ስምሪት ላይ የነበረ የልዩ ሐይል ወደ ጎንደር እንዲንቀሳቀስ የተደረገ ሲሆን …. በጎንደር የልዩ ሐይልና የአካባቢ ሚሊሻ እንዲሁም የመከላከያ ሰራዊት ምድቦች ማንም ይምጣ ማን ይህን ህዝብ ይንኩና እንተያያለን በማለት እርስ በእርሳቸዉ ተፋጠዉ ይገኛሉ።
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ ! ! !

በጎንደር እብናት የጦር መሣሪያ ማከማቻ መጋዘን መዘረፉ ተሰማ | 12 ክላሽንኮፍ ጎድሏል

$
0
0

File Photo

File Photo


ከልዑል ዓለሜ

ደቡብ ጎንደር ዞን እብናት ወረዳ ዛሬ ምሽት ማለትም በሐምሌ 22 /2008 ዓ.ም ለሐምሌ 23/2008 ዓ.ም አጥቢያ የፖሊስ ጣቢያ መጋዘን መዘርፋ መዘረፉ ተሰማ። ማንነታቸው ባልታወቁ ሰዎች የተዘረፈው መጋዝኑ የተለያዩ የጦር መሳሪያዎችን ናየፖሊስ አልባሳትን እንዲሁም የፖሊስ መገልገያ ቁሳቁሶችን የያዘ እንደነበር ታውቋል ። ዛሬ እስከ እኩለ ቀን ድረስ በወረዳው ፖሊስ አዛዥ ንጉሴ የሚመራ ቡድን የመሳሪያ ቆጠራ እያደረገ ሲሆን 12 ክላሽንኮፍ መሳሪያ አለመኖራቸው ተረጋግጧል።

ይህ የመሳሪያ ዘረፍ በሰሜን ጎንደር የተጀመረው የማንነት ጥያቄ በተነሳው አመፅ ጎንደር ውጥረት ውስጥ ባለችበትና ነገ ማለትም ሐምሌ 24/2008 ዓ.ም በሚካሄደው ህዝባዊ አመፅ ድራር ላይ መሆኑ የወረዳው ና የዞኑ አመራሮችን ድንጋጤ ውስጥ ከቷል ።

አንጋጋሪነቱም ጨምሯል ፤እስካሁን በድርጊቱ የተጠረጠሩ ሰወችን ለማደን የአመራሮቹ አይን በምሽቱ የጥበቃ ዘብ ያደረው የፖሊስ አባል ላይ አፍጥጠዋል ።

የጤፍ ዱቄትን ከጀሶና ሰጋቱራ ጋር ቀላቅለው እንጀራ በመጋገር የሚሸጡ መያዛቸው ተዘገበ |ሀኪሞች፤ ጀሶና ሰጋቱራ በጉበትና ኩላሊት ላይ ከፍተኛ ጉዳት ያደርሳል ይላሉ (የአዲስ አድማስ ጋዜጣ ዘገባ)

$
0
0

– ትላንት በልደታ ክ/ከተማ 5 ተጠርጣሪዎች ተይዘዋል
– ወንጀሉ ላለፉት 5 ዓመታት በከተማዋ በድብቅ ሲፈፀም ቆይቷል
– እንጀራው 30 በመቶ ጤፍ፣ 70 በመቶ ጀሶና ሰጋቱራ ተቀላቅሎ ይጋገራል
– ሀኪሞች፤ ጀሶና ሰጋቱራ በጉበትና ኩላሊት ላይ ከፍተኛ ጉዳት ያደርሳል አሉ
– በሁሉም ክፍለ ከተሞች ድርጊቱ እንደሚፈፀም ለማወቅ ተችሏል

(የአዲስ አድማስ ጋዜጣ ዘገባ) በአዲስ አበባ ከተማ የተለያዩ ክፍለ ከተሞች ጥቂት የጤፍ ዱቄትን ከጀሶ፣ ከሰጋቱራና ከደረቀ እንጀራ ዱቄት ጋር በመቀላቀል እየጋገሩ፣ ለገበያ የሚያቀርቡ ሰዎች ከየአካባቢው በቁጥጥር ሥር እየዋሉ ነው፡፡ እስከ አሁን በአቃቂ ቃሊቲ፣ በልደታ፣ በንፋስ ስልክ ላፍቶና በኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተሞች እንዲሁም በሰበታ ከተማ ውስጥ በተመሳሳይ ድርጊት ላይ የተሰማሩ ህገወጦች መያዛቸው ታውቋል፡፡ በትላንትናው ዕለት በልደታ ክ/ከተማ በተመሳሳይ ድርጊት ላይ የተሰማሩ 5 ተጠርጣሪዎችን ፖሊስ በቁጥጥር ስር አውሏል፡፡
injera
ህገወጦቹ 30 በመቶ የጤፍ ዱቄት፣ ቀሪውን 70 በመቶ ደግሞ ጀሶ፣ ሰጋቱራና የደረቅ እንጀራ ዱቄት በመቀላቀል እየጋገሩ ለሆቴሎች፣ ለሱፐር ማርኬቶች፣ ለሱቆችና ለምግብ ቤቶች በስፋት ሲያከፋፍሉ ቆይተዋል፡፡ ድርጊቱ በከተማዋ በሁሉም ክፍለ ከተሞች እየተፈፀመ እንደሚገኝና የተፈጨውን ሰጋቱራና የጀሶ ዱቄት ግብአቶች የሚያቀርቡ ግለሰቦች በስፋት እንደሚገኙ በቁጥጥር ሥር ከዋሉት ተጠርጣሪዎች መካከል አንዳንዶቹ ተናግረዋል፡፡

መነሻውን አቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ያደረገው ይኸው ህገወጦችን በቁጥጥር ሥር የማዋል ሂደት፤ በንፋስ ስልክ ላፍቶ ላፍቶና በኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተሞችም ቀጥሎ ሰንብቷል፡፡ ሰሞኑን በኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ ፈጥኖ ደራሽ ፖሊስ እየተባለ በሚጠራው የፖሊስ ካምፕ አካባቢ በሚገኘው የቅዱስ ጳውሎስ ቤተክርስቲያን ግቢ ውስጥ በተመሳሳይ ሁኔታ 13 ሰዎች በቁጥጥር ስር ውለዋል፡፡ ንብረትነቱ የቤተክርስቲያኑ በሆነውና አንድ ግለሰብ በኪራይ በወሰደው በዚህ ቤት ውስጥ በሰባት በርሜል የተቦካና ለጋገራ የተዘጋጀ ሊጥና በከረጢት ተሞልተው የተቀመጡ ጀሶዎች ተይዘዋል፡፡ ቀደም ሲል በዚሁ ክፍለ ከተማ አየር ጤና፣ ታቦት ማደሪያ እየተባለ በሚጠራው አካባቢ በተመሳሳይ መንገድ ጀሶና ሰጋቱራውን ከጤፍ ጋር እየተቀላቀሉ በመጋገር ለገበያ ሲያቀርቡ የነበሩ 8 ሰዎች በቁጥጥር ስር መዋላቸውንም የክፍለ ከተማው ፖሊስ አዛዥ ኮማንደር አወል ለአዲስ አድማስ ተናግረዋል፡፡

በአቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማ ወረዳ አንድ ውስጥ የተከናወነ የዚሁ ጤፍን ከጀሶና ሰጋቱራ ጋር ቀላቅሎ በመጋገር ለገበያ የማቅረብ ወንጀል መርማሪ የሆኑት ዋና ሳጅን ጎሽሜ አገኘሁ እንደገለፁልን፤ የድርጊቱ ፈፃሚዎች በአነስተኛና ጥቃቅን የተደራጁ አምስት ግለሰቦች ናቸው፡፡ ከእነዚህ ተጠርጣሪ ወንጀለኞች መካከል ሶስቱ በቁጥጥር ሥር ሲውሉ ሁለቱ እስከ አሁንም አልተያዙም፡፡ ተጠርጣሪዎቹ መንግስት በሰጣቸው ሼድ (መጠለያ) ውስጥ ጤፍን ከጀሶና ሰጋቱራ ጋር እየቀላቀሉ በመጋገር፣ ለሽያጭ የማቅረብ ሥራን ሲሰሩ ቆይተዋል፡፡ ከአንድ ግለሰብ ለፖሊስ በደረሰ ጥቆማ መሰረት፤ የመሥሪያ ቦታቸው በፖሊስ ሲፈተሽ ለመጋገር የተዘጋጀ 17 በርሜል ሊጥ፣ ከ20 ኩንታል በላይ የተፈጨና ለመቦካት የተዘጋጀ ዱቄት፣ በርካታ የሰጋቱራና የጀሶ ክምር መገኘቱን መርማሪው ገልፀዋል፡፡ በወቅቱ በጋገራውና በሊጥ ማቡካቱ ሥራ ላይ ተሰማርተው የነበሩ 12 ሰራተኞችና 3 የድርጅቱ ባለቤቶች በፖሊስ ቁጥጥር ሥር ውለዋል፡፡ የወንጀል ፈፃሚ ናችሁ ተብለው በቁጥጥር ሥር ከዋሉት 15 ሰዎች መካከል 12ቱ ሰራተኞች ድርጊቱን የፈፀሙት ታዘው ነው በሚል ከእስር የተለቀቁ ሲሆን ሶስቱ የድርጅት ባለቤቶች ግን በእስር ቆይተው፣ የ50 ሺህ ብር ዋስ ጠርተው ወጥተዋል፡፡ ሁለቱ ተጠርጣሪዎች አሁንም በፖሊስ አለመያዛቸው ታውቋል፡፡ ተጠርጣሪዎቹ በቁጥጥር ሥር በዋሉበት ወቅት ድርጊቱ በከተማዋ የተለያዩ አካባቢዎች እየተፈፀመ እንደሚገኝና ምንም አዲስ ነገር ወይም ወንጀል አለመሥራታቸውን ሲነገሩ ተሰምተዋል፡፡ ለምርት ግብአትነት የሚጠቀሙበትን የጀሶና የሰጋቱራ ዱቄት በአይሱዙ እያመጡ የሚያከፋፍሏቸው ሰዎች እንዳሉም ተጠርጣሪዎቹ ገልፀዋል፡፡ ከእስር የተለቀቁት አስራ ሁለቱ እንጀራ ጋጋሪዎች በወር 3000 ብር ደመወዝ እየተከፈላቸው ሲሰሩ እንደቆዩም ለማወቅ ተችሏል፡፡

በተጠርጣሪዎቹ ላይ የወንጀል ክስ ያቀረበው የሸማቾች ጥበቃ ባለስልጣን፤ ሶስቱ ተጠርጣሪዎች ባዕድ ነገርን ከጤፍ ጋር ቀላቅለው በመሸጥ በሚል ወንጀል ክስ አቅርቦ ሐምሌ 15 ቀን 2008 ዓ.ም ለፍ/ቤት ምስክሮቹን አሰምቷል፡፡ ፍ/ቤቱ የተባለው ባዕድ ነገር በጤና ላይ የሚያስከትለው ጉዳት መጠን ተመርምሮ ማስረጃው እንዲቀርብለት፣ በማዘዝ ለሐምሌ 26 (የፊታችን ማክሰኞ) ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡

በትናንትናው ዕለት ደግሞ በልደታ ክፍለከተማ ልዩ ስሙ አፍሪካ ህብረት አካባቢ የጤፍ ዱቄትን ከጀሶና ሰጋቱራ ጋር ቀላቅለው እንጀራ እየጋገሩ የሚሸጡ ግለሰቦችም በቁጥጥር ሥር ውለዋል፡፡ ተጠርጣሪዎች ምንም ዓይነት ህጋዊ ፈቃድ ሳይኖራቸው፣ ለአምስት ሆነው በተከራዩት ቤት ውስጥ የጀሶና የሰጋቱራ እንጀራ እየጋገሩ ለሽያጭ ያቀርቡ ነበር ተብሏል፡፡ ፖሊስ በትናንትናው ዕለት በተጠርጣሪዎቹ ቤት፣ ለጋገራ የተዘጋጀ አራት በርሜል ሊጥ እንዲሁም ሶስት ኩንታል ከሰጋቱራና ጀሶ ጋር የተደባለቀ የእንጀራ እህል ይዟል፡፡
በተመሳሳይ ሁኔታም ባለፈው ሳምንት በሰበታ ከተማ ቀበሌ 02 ልዩ ቦታው ዋቶ እየተባለ በሚጠራው አካባቢ ነዋሪ በሆነ አንድ ግለሰብ የጤፍ ዱቄት ከጄሶና ሰጋቱራ ጋር እየተቀላቀለ ተጋግሮ ለሽያጭ ሲቀርብ በፖሊስ መያዙ ታውቋል፡፡ ግለሰቡ በቁጥጥር ስር በዋለበት ወቅት በርካታ በርሜል ለጋገረ የተዘጋጀ ሊጥና ከሰጋቱራና ጀሶ ጋር የተቀላቀለ ዱቄት በቁጥጥር ሥር ውሏል፡፡

ከጀሶ፣ ሰጋቱራና የሻገተ ደረቅ እንጀራ ጋር እየተቀላቀለ የሚጋገረውና ለምግብነት እየዋለ የሚገኘው ‹እንጀራ››፤ በጤና ላይ የሚያስከትለውን ጉዳት አስመልከቶ አስተያየታቸውን እንዲሰጡን የጠየቅናቸው የውስጥ ደዌ ስፔሻሊስቱ ዶክተር አብርሃም ተስፋዬ፤ ሁኔታው እጅግ አስደንጋጭና ሰብአዊነት የጎደለው ድርጊት መሆኑን ገልፀው፤ የከፋ የጤና ችግር ማስከተሉ አይቀሬ ነው ብለዋል፡፡ ‹‹እንጀራው ለምግብነት ቢውል ይህን ዓይነት የጤና ችግር ያስከትላል ለማለት የንጥረነገሮቹን ምንነት ማወቅ ያስፈልጋል፡፡ በጥቅሉ ግን በጀሶ ውስጥ የሚገኘው ንጥረ ነገር፣ ነገሮችን የማኮማተር፣ የማጨማደድ ባህርይ አለው፡፡ በዚህ ሳቢያም ሰውነታችን ሊጨማደድና፣ የመጠን ለውጥ ሊያመጣ ይችላል፡፡ ንጥረ ነገሩ፣ በኩላሊት፣ ጉበትና በጨጓራ ላይ የሚያስከትለው የጤና ችግር በቀላሉ የሚገልፅ አይደለም ብለዋል፡፡

የቶም ከፍተኛ ክሊኒክ ባለቤት የውስጥ ደዌ ስፔሻሊቱ ዶ/ር አሚር መርዋን በበኩላቸው፤ ባዕድ ነገሮችን ወደ ሰውነታችን ውስጥ በሚገቡበት ወቅት እንደየ ንጥነገራቸው፣ ይዘታቸውና መጠናቸው የተለያዩ የጤና ችግሮችን ማስከተላቸው አይቀሬ መሆኑን ገልፀው ለባዕድ ነገሮቹ ተጋላጭነታችን እየጨመረ በሄደ መጠን የጉዳታችንም ልክ በዛው መጠን እየጨመረ እንደሚሄድ ተናግረዋል፡፡

‹‹ጀሶና ሰጋቱራ በአንጀት ውስጥ ገብተው መፈጨት የማይችሉ ከመሆኑም በላይ በጀሶ ውስጥ የሚገኘው ኬሚካል፣ የአንጀት ግድግዳን አልፎ ወደ ደም መሄድ ከቻለ፣ በውስጣዊ የሰውነታችን ክፍሎች ላይ ከባድ ጉዳት ያስከትላል፡፡ ለዚህ ደግሞ የመጀመሪያው ተጋላጭ ጉበታችን ነው፡፡ ጉበት በተፈጥሮው ጎጂና መርዛማ ነገሮች በደም አካማኝነት አልፈው ወደ ኩላሊትና ሳንባ እየሄዱ ጉዳት እንዲያስከትሉ የማድረግ ተግባር ያለው በመሆኑ፣ እነዚህ ኬሚካሎችን በሚያገኝበት ጊዜ ራሱን መስዋእት አድርጎ፣ ይዘቱን እንዲቀይሩ ያደርጋቸዋል፡፡ በዚህ ሣቢያም ጉበታችን ለጉዳት ይጋለጣል፡፡ አንዳንድ ጊዜ ከጉበት አቅም በላይ ከሆነ ወደ ኩላሊት በመሄድ የኩላሊት ጠጠርና መሰል ችግሮች እንዲከሰቱ ያደርጋል፡፡ በእንጀራው ውስጥ የሚጨመር የሻገተ እንጀራ ደግሞ አፍላቶክሲን በተባለው ንጥረ ነገር አማካኝነት ጉበት ላይ ጉዳት ያደርሳል፡፡ ይህ ደግሞ የገቡት ካንሰርን ሊያስከትልም ይችላል›› ብለዋል ዶ/ር አሚር፡፡

የሕወሓት መንግስት ማንኛውም ነገር ቢከሰት በእናንተ ላይ እርምጃ እወስዳለሁ ብሎ በማረሚያ ቤቱ ዝርዝራቸውን ቦርድ ላይ የተለጠፈው የ70 ታሳሪዎች ስም ዝርዝር

$
0
0

kaliti

bachlor
(ቢቢኤን ሰበር ዜና ሃምሌ 21/2008) ህወሃት መራሹ ኢህአዴግ ማንኛውም አይነት ነገር ቢከሰት በእናንተ ላይ እርምጃ እወስዳለሁ ብሎ በማረሚያ ቤቱ ዝርዝራቸውን ቦርድ ላይ የተለጠፈው የ70 ታሳሪዎች ስም ዝርዝር የለጠፈው ቢቢኤን ደርሶታል፡፡ በቦርዱ ላይ የተለጠፈው ስም ዝርዝራቸው፤ብሄራቸው፤የተከሰሱበት ዝርዝር ቀርቧል ፡፡

ከዚህም ስም ዝርዝር ውስጥ በተራ ቁጥተር 1 የኡስታዝ አህመዲን ጀበል በተራ ቁጥር 6 እና 7 ደግሞ ኡስታዝ ሙሃመድ አባተ እና በድሩ ሁሴን ሲገኘበት በተራ ቁጥር 27 ደግሞ ካሚል ሸምሱ ተጠቅሷል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ በኦነግ የተከሰሱ የኦሮሞ ተወላጆች፤በግንቦት ሰባት እና ቅንጅት የተከሰሱ የአማራ ተወላጆች፤የደቡብ ተወላጆች እና የሶማሌ ተወላጅ ይገኝበታል ፡፡ በአሁኑ ጊዜ በታሳሪዎቹ ላይ ጫና እየተደረገ መሆኑም ታውቋል፡፡ ከዚህ በተጨማሪም በቃሊቲ የነበረው የጨለማ ቤት አንድ ብቻ ሲሆን በአሁኑ ጊዜ 4 የጨለማ ቤቶች መሰራታቸው ታውቋል፡፡ ጠያቂዎችም ከሚስት እና ልጅ ውጭ እንዳይጠይቃቸው መደረጉም ታውቋል፡፡ ህወሃት መራሹ ኢህአዴግ በታሳሪዎቹ ላይ የሚያደርሰውን ጫና ያቆም ዘንድ ሁሉም ኢትዪጲያ በጋራ በአንድነት ተቃውሞውን እንዲገልፅ ታሳሪዎች ገልጸዋል፡፡

ቦርዱ ላይ የተለጠፈው ስም ዝርዝር ከዚህ በታች ቀርቧል፡፡
ሙሉ ስም ብሄር የተከሰሰበት:-

1.ኡስታዝ አህመዲን ጀበል ብሄር ኦሮሞ የተከሰሰበት በሙስሊሙ
2 መስፍን ኢታና ኦሮሞ ኦነግ
3 ጣሂር ሸህ አህመድ ኦሮሞ ኦነግ
4 በሺር አህመድ ኦሮሞ ኦነግ
5 ፈየራ ከተላ ኦሮሞ ኦነግ
6 ሙሃመድ አባተ አማራ በሙስሊሙ
7 በድሩ ሁሴን አማራ በሙስሊሙ
8 መሳይ አበራ አማራ
9 ሰይድ ሀሰን አሮሞ ኦነግ
10 ጎዳና ደዮ አሮሞ ኦነግ
11 ለአለም አበራ ደቡብ
12 አሸናፊ ገብረ ሚካኤል ደቡብ
13 እንየው ተሾመ ኦሮሞ
14 ሄኖክ ደሳለኝ አማራ
15 ሰለሞን ገላን አማራ
16 ብርሃኑ ክብረት አማራ
17 ሃብቴ ሹሜ አማራ
18 ግርማ ጎተሬ ኦሮሞ
19 ዳንኤል ብርሃን
20 አቤል ግዛቸው አማራ
21 ሸዋፈራኁ ጫኔ አማራ
22 ገብሬ ሲሳይ አማራ
23 ሶፎኒያስ ነጎ አማራ
24 ቢኒያም ጌታቸው አማራ
25 ሀሰን አብዱልቃድር ሶማሌ
26 ተመስገን ባይለየኝ አማራ በግንቦት ሰባት
27 ካሚል ሸምሱ ኦሮሞ በሙስሊሙ
28 ቴዎድሮስ መከተ ኦሮሞ
29 ገዛሃኝ አለሙ ኦሮሞ
30 ቴዎድሮስ ነጋ አማራ
31 ዮሴፍ ጌታሁን ኦሮሞ
32 ሚኪያስ አበበ አማራ
33 ታደሰ አየለ አማራ
34 እያሱ ዳንኤል
35 ዪሴፍ ዘውዴ አማራ
36 ዝም በላቸው ግርማ አማራ
37 ቢኒያም ፍሰሃ
38 ሙሃመድ አርጋው ደቡብ
39 ይትባረክ ጥበብ አማራ
40 ሰለሞን ታደሰ አማራ
41 ዳንኤል ከበደ ኦሮሞ
42 አብዱ ተሾመ አማራ
43 ቢኒያም ገረመው አማራ
44 አንተነህ አፖሎ አማራ
45 የሺዋስ ምትኩ አማራ
46 ጎሺራድ ጸጋ አማራ
47 እጹብ ተፈራ አማራ
48 አንደርሰን በላይ አማራ
49 ዘካሪያስ ገብረ ጻድቅ አማራ
50 ታረቀኝ ሃይሉ አማራ
51 ፈየራ በቀለ ኦሮሞ
52 ሰለሞን ደጀነ አማራ
53 ጃተኒ ኬሉ ኦሮሞ
54 ይርጋ ክበበው አማራ
55 አወል ጃተኒ ኦሮሞ
56 ደመላሽ እሸቱ አማራ
57 አለሙ ነጎ ኦሮሞ
58 ብሩክ ሃይሌ አማራ
59 ሲሳይ ገመቹ ኦሮሞ
60 ፍቃዱ ተሾመ አማራ
61 ግሩም ታምሩ አማራ
62 ቴዎድሮስ አድማሱ አማራ
63 ወሰን አድማሱ አማራ
64 ሲመክት አሰፋ አማራ
65 በሪንሁን አገባቸው አማራ
66 ሙሃመድ አስናቀ አማራ
67 ካሳሁን ጌጡ አማራ
68 ወንዶሰን ጫኔ አማራ
69 ደምሰው አንተነህ አማራ
70 ወጋየሁ ነጋሽ ኦሮሞ

በዞን አንድ የተለጠፉት ስም ዝርዝሮች እነዚህ ሲሆኑ ይህንም ማረጋገጥ የፈለገ አካል ቃሊቲ በቃሊቲ ተለጥፎ ይገኛል ፡፡ ህወሃት መራሹ ኢህአዴግ በታሳሪዎቹ ላይ የሚያደርሰውን ጫና ያቆም ዘንድ ሁሉም ኢትዪጲያ በጋራ በአንድነት ተቃውሞውን እንዲገልፅ ታሳሪዎች ገልጸዋል፡፡ ቢቢኤን ተጨማሪ መረጃዎችን እየተከታተለ የሚያቀርብ ይሆናል::

 

Source: ቢቢኤን ሰበር ዜና ሃምሌ 21/2008

ስደተኞች ወደ ምዕራብ አገሮች እንዳይፈልሱ ለመከላከል የአውሮፓ ህብረት ለወያኔ አገዛዝ የሰጠው የገንዘብ ስጦታ ውጤት አይኖረውም ተባለ (የፍኖተ ዴሞክራሲ ራድዮ አጫጭር ዜናዎች)

$
0
0

ሐምሌ 22 ቀን 2008 ዓ.ም.
ርዕሰ ዜና
 ስደተኞች ወደ ምዕራብ አገሮች እንዳይፈልሱ ለመከላከል የአውሮፓ ህብረት ለወያኔ አገዛዝ የሰጠው የገንዘብ ስጦታ ውጤት አይኖረውም ተባለ
 ባለፈው ማክሰኞ በካይሮ ከተማ ከተመድ ጽ/ቤት ፊት ለፊት ሁለት ኢትዮጵያውያን በእሳት ተቃጠሉ
 በተለያዩ ቦታዎች የሚካሄዱት ሕዝባዊ እንቅስቃሴዎች እንደቀጠሉ ናቸው
 በሶማሊያ ሶስት የወያኔ ወታደሮች በአልሸባብ ተገደሉ
 ተመድ በሰሜን ምስራቅ ናይጄሪያ የሚሰጠውን የሰብአዊ እርድታ ለጊዜው አቋረጠ
 10 የሰብአዊ እርዳታ ድርጅቶች ተመድ በደቡብ ሱዳን ጠንካራ እርምጃ እንዲወስድ ጠየቁ
 የዚምባብየው ፓስተር ሰላማዊ የሆነ ሕዝባዊ ተቃውሞ ጠሩ
ዝርዝር ዜናዎች

Mediterranean-troubles
 ወደ ደቡብ አፍሪካም ሆነ ወደ ምዕራብ አገራት በብዛት ከሚሰደዱት መካከል ጎላ ያለ ቁጥር ያላቸው ስደተኞች የሚመጡት ከኢትዮጵያ መሆኑ ሲታወቅ የስራ ዘርፎችን በመክፈት የስደተኛውን ቁጥር ለመቀነስ በወሰደው ፖሊሲ የአውሮፓው ህብረት 20 ሚሊዮን ዶላር ለወያኔ አገዛዝ የሰጠ መሆኑ ታውቋል። በኑሮ ችግር ምክንያት በ ስደተኞች አገር ለቀው መውጣታቸው የማይካድ ቢሆንም ከኢትዮጵያ የሚወጡት በርካታዎቹ አገዛዙ በሚያደርስባቸው በደልና ግፍ መሆኑ የሚታወቅ
በመሆኑ የተሰጠው ገንዝብ ስደተኞችን ለማስቀረት እምብዛም የማይረዳ መሆኑን ብዙዎቹ ይናገራሉ።

 ባለፈው ማክሰኞ ሐምሌ 19 ቀን 2008 ዓም. በግብጽ የተመድ ጽ/ቤት ፊት ለፊት በእሳት የተቃጠሉት ኢትዮጵያውን ቁጥር ሁለት መሆኑን የተላያዩ የግብጽ ጋዜጦች በአምዶቻቸው ላይ አስፍረው አውጥተዋል። በእሳቱ አደጋ የተጎዱት ጥገኝነት የሚጠይቁ ኦሮሚኛ ተናጋሪ ኢትዮጵያውያን መሆናቸውንና የሁለት ልጆች እናት የሆነች ሴት ራሱን አቃጥሎ የነበረውን ሌላ ሰው ለማዳን ባደረገችው ሙከራ ተቃጥላ የሞተች መሆኑን ለማወቅ ተችሏል። ካይሮ የሚገኘው የተባበሩት መንግስት ድርጅት የስደተኞች ጉዳይ ጽ/ቤት ረቡዕ ሐምሌ 20 ቀን ማምሻውን ባወጣው መግለጫ በሴትዮዋ መሞት የተሰማውን ሀዘን ገልጾ ለስደተኞች ብስጭትና ቁጣ የማመልከታችዎች ጊዜ መጓተና መሆኑንና ችግሩ ሊከሰት የቻለውም ቁጥራችው በጣም ከፍተኛ መሆኑን በመጥቀስ ለማብራራት ሞክሯል። በግብጽ ውስጥ በተመድ የስደተኞች ኮሚሽን በኩል የጥገኛነት ማመልከቻ ተቀባይነት እንዲያገኝ ለማድረግና ሂደቱን ለማስጀመር በርካታ ወራት አንዳንዴም ዓመታትን እንደሚወስድ ይታወቃል።

 በተለያዩ ቦታዎች የሚካሄዱት ሕዝባዊ እንቅስቃሴዎች አሁንም እንደቀጠሉ እየተነገረ ነው። በምዕራብ ሀረርጌ በግራዋ የወያኔ አግአዚ ጦር አባላት በተኮሱት ጥይት የተመታ አንድ ወጣት የሞተ መሆኑ ተዘግቧል። በምዕራብ አርሲ በአዳባ በዛሬው ቀን ተመሳሳይ ህዝባዊ የተቃውሞ እንቅስቃሴ መካሄዱ ተዘግቧል።

 በሱማሊያ የባኮል ግዛት ዋና ከተማ ከሆነው ከሁዱር 45 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በሚገኘው ሞራጋቤ በተባለው ቦታ ላይ የአልሸባ ኃይሎች በሶማሌ መንግስት ወታደሮችና በአፍሪካ ህብረት የሰላም አስከባሪ ኃይል ላይ ባካሄዱት ጥቃት አምስት ወታደሮች መገደላቸውና ከአምስቱ ሶስቱ የወያኔ ወታደሮች መሆናችው ሸበሌ ኒውስ የተባለው የዜና ምንጭ የአይን እማኞችን መረጃ ዋቢ በማደረግ ገልጿል። በውጊያው ምክንያት ነዋሪዎች አካባቢውን ለቀው የወጡ ሲሆን ለበርካታ ሰዓቶች
ከተደረጉ በቀላልና በከባድ መሳሪዎች የተኩስ ልውውጦች በኋላ የአልሸባብ ኃይሎች ቦታውን ለቀው የሄዱ መሆናችው ተገልጿል። ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በሶማሊያ ውስጥ የሚሞቱና አካለ ስንኩላን የሚሆኑ የወያኔ ወታደሮች ቁጥር ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መሄዱን ምንጮች እየገለጹ ነው፡:

 በናይጄሪያ ሰሜን ምስራቅ የቦኮ ሃራም ታጣቂዎች በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የእርዳታ ኮንቬይ ላይ ጥቃት ፈጽመው ጉዳት ያደረሱ መሆናቸው ታውቋል። በጥቃቱ የተመድ የእርዳታ ሰጭ ድርጅት አባል የሚገኝበት ሶስት ሰላማዊ ሰዎች ሁለት ወታደሮች የቆሰሉ መሆናቸው የተነገረ ሲሆን ተመድ ወደ ቦርኖ ግዛት የሚያደርገውን የሰብአዊ እርዳታ ለጊዜው ያቋረጠ መሆኑ ታውቋል። በቦኮ ሃራም ጥቃት ምክንያት ከቤት ንብረታችው ተፈናቅለው በስደተኛ ጣቢያዎች የሚኖሩት ዜጎች ቁጥር
ከሁለት ሚሊዮን በላይ ሲሆን አብዛኞች ህጻናት በምግብ እጥረት እንደሚሰቃዩ ተነግሯል። ላለፉት ሰባት ዓመታ የሽብር ተግባሮችን ሲያካሂድ የቆየው ቦኮሃራም ባካሄዳቸው ተከታታይ ጥቃቶች ከ20 ሺ ሰዎች በላይ ህይወታቸውን ያጡ መሆናቸውንና በሚሊዮን የሚቆጠሩ ዜጎች ደግሞ መስደዳቸው ይታወቃል።

 በደቡብ ሱዳን እርዳታ በመስጠት ላይ የሚገኙ አስር የሰብአዊ እርዳታ ሰጭ ድርጅቶች የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰላም አስከባሪ ኃይል በደቡብ ሱዳን ጠንካራ እርምጃ እንዲወስድ በመጠየቅ የጋራ መግለጫ አወጡ። ኦክስፋም፤ ኬር፤ ኢንተርናሽናል ሬስኩ ኮሚቴ የተባሉት የሰብአዊ እርዳታ ሰጭ ድርጅቶች የሚገኙበት ይኸው ስብስብ ባወጣው የጋራ መግለጫ የመንግስት ኃይሎች በሰላማዊ ሰዎች ላይ የሚወስዱት የግፍና የጭካኔ እርምጃ በተለይም ከፍተኛ ደረጃ ላይ የደረሰ መሆኑንና
ለችግሮችም እርዳታ ለማድረስ የማይቻልበት ደረጃ መድረሱን በመጥቀስ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰላም አስከባሪ ኃይል ኃይሉን አጠናክሮ እርምጃ መውሰድ አለበት ብለዋል። በደቡብ ሱዳን ውስጥ የሚገኙ 12 ሺ የተመድ ወታደሮች ሰላማዊ ሰዎችን ለመጠበቅ የኃይል እርምጃ እንዲወስዱ የተፈቀደላችው ቢሆንም ኃይላቸውን ተጠቅመው ሰላማዊ ሰዎችን ሲጠብቁ አልታዩም ብለዋል። በደቡብ ሱዳን 4.8 ሚሊዮን ሕዝብ በምግብ እጥረትና ረሃብ የሚሰቃይ ሲሆን ይህም ከሕዝቡ ቁጥር ግማሹ ነው ተብሏል። ሁኔታው በዚህ የሚቀጥል ከሆነ እርዳታ ለመስጠት የሚቻልበት ሁኔታ እንደሌለ መግለጫው ገልጾ ከፍተኛ እልቂት ሊከተል እንደሚችል አስጠንቋል።

 ህይወታቸውን ከአደጋ ለመጠበቅ ወደ ደቡብ አፍሪካ የተጓዙት ፓስተር ኢቫን ማዋሪሬ ሐሙስ ሐምሌ 21 ቀን 2008 ዓም በአንድ ዩኒቨርስቲ ውስጥ ለተሰበሰቡ በርካታ የዚምባብዌ ዜጎች ባደረጉት ንግግር ዚምባዊ ውስጥ ያለው ሁኔታ በጣም አሳዛኝ መሆኑን ጠቅሰው ሕዝቡ በትግሉ ነጻነቱን መጎናጸፍ አለበት ብለዋል። ከአገራቸው የወጡት በህይወታችው ላይ አደጋ በመምጣቱ መሆኑን ገልጸው ሰላማዊ የሆነው ተቃውሞ መቀጠል አለበት የሚል መልክት አስተላልፈዋል። በዚምባዌ
የታወቀው የአርበኞች ማህበር ቃል አቀባይ በመንግስት ኃይሎች በቁጥጥር ስር መዋላቸው መዘገባችን ይታወሳል።


በደቡብ ጎንደር እየተሠራ ያለ ግድብ ፈርሶ ቁጥራቸው ያልታወቀ ሰዎች ሕይወት አለፈ

$
0
0

mesafint bazezew

ከመሳፍንት ባዘዘው
በደቡብ ጎንደር ፋርጣ፣ ፎገራ፣ እብናትንና ሊቦ ከምከም ወረዳዎችን የሚያዋስነው እርብ ወንዝ ላይ በመገንባት ላይ ያለ ግድብ በመደርመሱ ቁጥራቸው ያልታወቀ ሰዎች ሕይወት ማለፉ ተሰማ::

ዛሬ ጁላይ 30, 2016 ዓ.ም ይኸው እርብ ወንዝ ላይ የሚሰራውና 85 ሜትር ርዝመት ያለው ግድብ “ኢንቴክ ታውሩ ” በመደርመሡ ቁጥራቸው ያልታወቀ ሲሆን በህንፃው ፍርስራሽ ተዳፍነው አሰቃቂ ጉዳት የደረሰባቸውን ወገኖች አስክሬን መለየት አስቸጋሪ እንደሆነባቸው የአካባቢው ነዋሪዎች ለዚህ ዜና ዘጋቢ ገልጸውለታል፡፡

የዓይን እማኞች እንደሚሉት ከሆነ በዚህ አደጋ የቆስሉ ወገኖች ወደ ባህር ዳር እና አዲስ ዘመን እብናት ጤና ጣቢያዎች በመወሠድ ላይ ይገኛሉ ፡፡ በፍርስራሹ የተዳፈኑትን የማወጣት ርብርብም እየተደረገ ነው።

“ወገኖቻችንን ጥራት በሌለው ግንባታ ላይ ያለ ምንም የአደጋ መከላከያ ቁሳቁስ ስራ እንዲሰሩ እና ለሞት እንዲዳረጉ ያደረገው አካል በቀጥታ ተጠያቂ ይሆናል። ነብስ ይማር ! መፅናናቱን ይስጠን!” ሲል አስተያየቱን በመስጠት የዚህ ዜና ዘጋቢ ዘገባውን ያጠናቅቃል::

በልማት እናበሙስና የሚፈፀሙ ደባዎች –ሙላት በላይ

$
0
0

Woyaneወያኔ ኢትዮጵያን በተለይም ዐማራን ለማጥፋትዓቅዶ ለዕቅዱ ማስፈፀሚያ ከነደፋቸዉ ሥልቶች መካከል

1 ልማት የዐማራዉን ቅርስ ታሪክ ገዳማት ተቋማት ወዘተ ለማፍረስ ለስዉር ደባዉ መሸፈኛ የሚጠቀምበትና ህዝቡን ልማታዊ መንግስት ነኝ በማለት መልፈፍና በማይተገብረዉ ልማት ስም ደባዉን መፈፀም ነዉ ፡፡ ለዚህም መረጃ የሚሆነዉ ከአላጡት ቦታ የዋልድባን ገዳም በማፍርስ ባህታዊያንንና መነኮሳትን በመደብደብ በማሰደድ ባዶ ባድማ ማድረጉ ነዉ፡፡ ይህን ለምሳሌ ጠቀስኩ እንጅ በሁሉም የዐማራ ክልል አልፎም በኢተዮጵያ መፈፀሙን ሁሉም ኢተዮጵያዊ የሚያዉቀዉ ነዉ፡፡ ለዚህም ነዉ እነስብሃት ነጋ እነሳሞራ የኑስ ዐማራንና ኦርቶዶክሰ ሃይማኖትን ገድለን ቀብረነዋል እያሉ የሚፎክሩት

2 ሙስና ወያኔን እና መሰሎቹን ለማበልፀግ አገሪቱን መከፈል ከማትችለዉ እዳ ለመጣል እና የዘላለም ደሃና ጥገኛ ለማድረግ የሚጠቀሙበት ሥልታቸዉ ሲሆን በሌላ በኩል ደግሞ እነሱ በቢሊዮን የሚቆጠር ገንዘብ ሲዘርፉ ለነሱ ዓላማ አሰፈፃሚ ለሆኑት የአማራና የኦሮሞ ልጆች በምስልነት ለተቀመጡበት ወንበርና ስልጣን የነሱን ፍርፋሬ በመልቀም እነዲጠቀሙ በር መክፈትና በዚሀ ፍርፋሪ አመካይነት ሰጥለበጥ ብለዉ ህሊናቸዉን ሽጠዉ ለወያኔ እነዲያገለግሉ ማድረግ ከዚህ ወጣ ከአሉ በዚሁ ፍርፋሪ ጥቅማቸዉ መነሻነት በሙስና አሳቦ ለማሰር ለመግረፍ ለማባረር እነዲያም ሲል ለመግደል የሚጠቀሙበት ስልት ነዉ ለምሳሌ አዲሱ ሃይማኖተኛ ታምራት ላይኔ ቡዳ እንደበላዉ እየለፈለፈ የተባረረዉ በዚህ ስልት ነዉ ፡፡

ስለዚህ የዐማራም ሆነ የኦሮሞ ተወላጅ የሆናችሁ የህዝብ ምስሎች በአሁኑ ሰዓት የህዝብ ዐመፅ እየተፋፋመ ስለሆነ በአጣብቂኝ ዉስጥ መሆናችሁን አዉቃችሁ ከሰፊዉ ህዝብ ጎን መሰለፍ ለእናንተ እንደሚበጃችሁ ስንገልፅ ከሐምሌ8/2016ዓም  ጀምሮ ከወያኔ በስተቀር ማንም የሚታመን ባለመሆኑ የክልል መንግስታት ተብለህ የተሰየምክበትን ናየማትጠቀምበትን የይሰሙላ ሥልጣን ተቀምተህ ለወያኔ ቤሰብ የሆነ ይተካበታል የክልልመንግስታት የሚባሉት በስያሜ ብቻ እንጅ በአፈፃፀም የፌደራል ጠቅላይ ፍርድቤት ከፖሊስና ከደህንነት ስራተኞች ጋር በመጣመር ሽብረተኛ በሚል ሰያሜ ያወጡትን ህግ ከትግራይ በስተቀር በሁሉም ክልሎች ተፈፃሚ እንዲሆን በምስልነት ለማጨብጨብ የተሰየመዉ ፓርላማ ተብየ ወያኔ የአወጣዉን ያዘጋጀዉን የመጥለፊያ ህጎች በጭብጨባ አፀድቆ አንድ ባንድ እጅህ ተይዞ እንደኮርማበሬ ከመቀጥቀጥህ በፊት ምርጫህን በአስቸኳይ እንድታስተካክል ወገንህ ጥሪ አድርጎልሃል፡፡

ወያኔ ነገሮችን ሁሉ በሱ እጅ ብቻ ለማድረግ ማሰቡን መረጃ የሚሆነዉ ሰሞኑን በጎንደር የተፈፀመዉ ድርጊት ነዉ፡፡ የኸዉም

1 የክልል መንግስታት ተብየዉ ሳይነገረዉና ሳያዉቀዉ ወያኔወች ዘዉ ብለዉ ገብተዉ ሰዉን እነደበግ ግልገል ለመዝረፍ መሞከራቸዉ

2 ክልሎች የራሳቸዉ ጦር እያላቸዉ የየክልሎች ጦር የወያኔ ዘር ባለመሆናቸዉ እምነት ሳየጣልባቸዉ በመቅረት በየክልላቸዉ ለሚፈጠረዉ ችግር ለችግሩ መፍታት ባለቤት አለመሆናቸዉ

3 በ7/20/2016ዓም    በጎንደር ከተማ ለተደረገዉ የእግር ኳስ ጨዋታ ለፀጥታ ጥበቃ ከፌደራልእና ከወያኔ ቅጥረኞች በስተቀር የክልሉ ታጣቂ በሙሉ መሳሪያህን ይዘህ ከቤትህ እንዳትወጣ አርፈህ ተቀመጥ ወየልህ መባሉ እና ፀጥ ብሎ መቀመጡ

4 የደርግን መንግስት ለመጣልና በህዝባዊ መንግስት ለመተካት ሁሉም ኢትዮጵያዊ የታገለበትን የትግል ዉጠየት ሌላዉን በመካድ እኛ ወርቆቹ ታግለን ያመጣነዉን እኛ ብቻ እንደፈለግን በማድረግ እንጠቀምበታለን እንጅ ለደርግ እርዝራዥ ለአለፈዉ ሥርዓት ናፋቂ  ለነፍጠኞች አንለቅም በማለት ህዝብን አስገድዶ በማሰለፍ የሚያሰሙት መፈክር ወዘተ ናቸዉ ቀስቅስ

5ቱን የአፍሪካ ውብና ደማቅ ከተሞች ይተዋወቁ

$
0
0

Luanda

ከታምራት ሲሳይ

1. ሉዋንዳ

የአንጎላ ዋና ከተማ ሉዋንዳ በአፍሪካ በነዳጅ ምርት፣ የባህር ወደብና የአስተዳደር ማዕከል ናት:: በአለፉት አስርት ዓመታት ከአፍሪካ አገራት የላቀ ዕድገት አሳይታለች::

በቻይና የኢንቨስትመንት ኮርፖሬሽን ግንባታ እንደ ምዕራባዊያን ከተሞች የመጠቀች ሆናለች::

adagir

2. አጋዲር

የሞሮኮ አንዷና ዋነኛ ከተማ ናት:: ከተማዋ በ1960 በርዕደ መሬት ከተመታች በኋላ እንደገና የተገነባች ናት:: አሁን የባህር ዳርቻ ያላት የጎብኝዎችን ቀልብ ከመላው ዓለም የምትስብ ተመራጭ ከተማ ከሥራ ቦታ በሚጠፉ ሰራተኞች የተዘጋው ሆናለች::

Nairobi

3. ናይሮቢ

የኬኒያ መዲና እና ትልቋ ከተማ ናት። ከምስራቅ አፍሪካ ከተሞች በህዝብ ብዛትም ቀዳሚ ናት:: ከአፍሪካ በፖለቲካም ሆነ በምጣኔ ሀብት ዕድገት ከመሪ ከተሞች ተርታ ተሰልፋለች:: የንግድ እንቅስቃሴዎች የሚበዙባትና ዓለማቀፍ ተቋማት የከተሙባት በመሆኑ ደማቅ አድርጓታል።

Legos

4. ሌጐስ

በህዝብ ብዛቷ ከናይጀሪያ ቀዳሚ የአገሪቱ መዲናም ናት:: የሌጐስ ደሴት ከሰማይ ጠቀስ ፎቆችዋና በጅምላ ንግድ ማዕከልነቷ ትታወቃለች:: ከበርካታ ብሔሮቿ ውበት ጋር ተዳምሮ ከተማዋ ውብና ደማቅ መሆን አስችሏታል።

Cairo Egypt

5. ካይሮ

የስልጣኔ መናኸሪያዋ፣ የግብፅ ዋና ከተማ ካይሮ ከመካከለኛው ምስራቅ አገራት እና ከአፍሪካ ሁለተኛዋ ትልቋ ከተማ ናት:: ከተማዋ የ24 ሰዓት ከተማ ተብላም ትታወቃለች:: ካይሮ 24 ሰዓት ሙሉ ደምቃ ውላ ታነጋዋለች።

በጎንደር ህዝብ አደባባይ ወጥቶ እየጠየቀ ነው |ለኦሮሞ ወገኑ አጋሩን ገልጾ ሕዝብ ፍትህ ጠየቀ

$
0
0


(ዘ-ሐበሻ) ሕወሓት የሚመራው መንግስት ከቀናት በፊት የዛሬውን ሰላማዊ ሰልፍ ለማስተጓጎል “ሰልፉ አልተፈቀደም; የሚደረግም ሰላማዊ ሰልፍ የለም” በማለት በየሚዲያው ፕሮፓጋንዳ ሲነፋ ቢቆይም የጎንደር ሕዝብ ግን ሕገመንግስቱ በፈቀደልኝ አንቀጽ መሰረት ሰልፍ እንደማደርግ ማሳወቅ እንጂ ማስፈቀድ የለብኝም በሚል ዛሬ በነቂስ ወጥቶ ጩኸቱን አሰምቷል:: በልዩ ሃይልና በፖሊስ ሰራዊት የተከበበውን የጎንደሩን መስቀል አደባባይ በማስለቀቅ የጎንደር ህዝቡ በነቂስ ወጥቶ ድምጹን ሲያሰማ ነበር::

ዋነኛው ጥያቄ ወልቃይት ጠገዴ አማራ ነው የሚል ጥያቄ ቢሆንም በዛሬው ሰላማዊ ሰልፍ ግን ጥያቄዎች አደግ ብለው “በኦሮሚያ ክልል የሚደረጉ ግድያዎች በወድሞቻችን ላይ የሚፍጸሙ ናቸውና ይቁሙ” “የፖለቲካ እስረኞች ይፈቱ” “የትግራይ ወሰን ተከዜ ነው፤ ትግሬ እንጂ ትግራይ ተከዜ ተሻግሮ አያውቅም፤” በሃገሪቱ ፍትህና እኩልነት ይስፈን.. “ኮለኔሉ ይፈቱ”.. “የወያኔ ተላላኪ ህወሃት እንጂ ወልቃይት አማራ አደለም።” “ዐማራን መግደል ይቁም” “”የትግራይ ህዝብና ህወሓት ለየብቻ ናቸው” ፣ “ወልቃይት ጠገዴ ዐማራ ነው፣” “ኮሚቴዎች ይፈቱ”፤ “የታሰሩት የሙስሊም ኮሚቴዎች ይፈቱ”፣ በኦሮሚያ የሚደረገው ግድያ ይቁም፣ አቶ በቀለ ገርባ ይፈቱ… ወዘተ የሚሉ ጥያቄዎች ተስተናግደዋል::

በብዙ ሺህ የሚቆጠር የጎንደር ሕዝብ የወጣበት ይህ ሕዝባዊ ትዕይነት ሕዝብን ዓላማውን ለማሳት የሕወሓት መንግስት የሚቻለውን ሁሉ ቢያደርግም የጎንደር ሕዝብ ግን አክሽፎታል:: በተለይም በዛሬው ሰላማዊ ሰልፍ ላይ እናቶች በየቦታው ውሃ ይዘው በመቆም ለጠሙ ሰለፍኞች ሲያጠጡ በቭዲዮ ጭምር የተለቀቁ መረጃዎች አሳይተዋል:: ከዛሬው ሰልፍ የተወሰኑ ፎቶዎችን እንጋብዛችሁ:: ተጨማሪ መረጃዎችን ይዘን እንመለሳለን::

Gonder6Gonder2Gonder1Gonder5Gonder3Gonder8Gonder4Gonder9

 

የእስቴ ዐማራ ለቀጣይ እሁድ ዳግም ቀጠሮ ይዞ ሰልፉን ጨረሰ

$
0
0

Gonder6
ሙሉቀን ተስፋው
ከአንዳቤት፣ ቆማ ፋሲለደስ፣ ስማዳ፣ ሎዋየ፣ አርብ ገበያ (ደራ)፣ ግራርያ ማኅደረ ማርያም ለሚኖረው ዐማራ ጥሪ በማስተላለፍ በቀጣይ እሁድ ነሐሴ 1 ቀን 2008 ዓ.ም.የዐማራ ተጋድሎ ሰልፍ ለማድረግ ተስማምቶ የዛሬውን ሰልፍ ጨርሷል።

አስተባባሪ ኮሚቴዎች እና የመፈክር አዘጋጅ አባላት በሕዝብ ተመርጠዋል። ነሐሴ 1 ቀን 2008 ዓም በቅሎዎችና አጋሰስ ፈረሶች ይሸለማሉ፤ የዐማራ ሕዝብ አንድነት ይዘካራል። ከእስቴ፣ ደራ፣ ፋርጣና ስማዳ ወረዳዎች የተውጣጣ ከሁለት መቶ ሺህ በላይ ዐማራ የመካነኢየሱስ ከተማን የዛሬ ሳምንት ያደምቃል።

ይህ ሁሉ የመጨረሻው መጀመሪያ ነው!!

ከአዲስ አበባ ሀረርና ጅጅጋ የሚወስደው መንገድ ተዘጋ |አጋዚ በአወዳይ ሰላማዊ ሰልፈኞችን በጥይት አቆሰለ | Updated

$
0
0

oromia
(ዘ-ሐበሻ) ጎንደር በሰላማዊ ሰልፍ በተቀወጠበት በዛሬው ዕለት ምስራቅ ሐረርጌ አወዳይ ከተማም እንዲሁ ሕዝባዊው ተቃውሞ ገንፍሎ መውጣቱ ተሰማ::

ሕዝቡ በሰላማዊ መንገድ ወጥቶ ተቃውሞን ባሰማበት በዛሬው የአወዳይ ከተማ ተቃውሞ በስፍራው የነበረው የአጋዚ ሰራዊት 4 ሰዎችን ክፉኛ ማቁሰሉ ተሰምቷል::

የሕዝባዊ ተቃውሞው እጅግ በመጠንከሩ ሕዝቡ ከአዲስ አበባ ሃረርና ጅጅጋ የሚያገናኘውን መንገድ በድንጋይ; በ እንጨትና በተለያዩ ቁሳቁሶች እንደዘጋጋቸው የደረሱን መረጃዎች ይጠቁማሉ:: በዛሬው ተቃውሞ በአጋዚ ጥይት ከቆሰሉት መካከል አህመድ የሱፍ; ሙአዝ አብዱልሃሚድ ኡመር; ባርክሌና በየነ ደሜሾ የሚባሉ ወጣቶች እንዳሉበት ታውቋል::

አሁን በደረሰን መረጃ በአወዳይ በአጋዚ ጥይት ተቀጥቅጦ የቆሰለው በየነ ዳሚሾ የተባለው ወጣት በሐረር ሆስፒታል ሕይወቱ ማለፉ ተሰምቷል::

በጎንደር፣ በማክሰኝት፣ በምዕራብ በለሳና በበምዕራብ እስቴ ታላላቅ ሰልፎች ተደርገዋል | 4 አጫጭር መረጃዎች

$
0
0

amhara
ከሙሉቀን ተስፋው

1. በጎንደር ከተማ ከአምስት መቶ እስከ ስምንት መቶ ሺህ የሚቆጠር ሕዝብ ሰልፉን ማድመቁ የታወቀ ሲሆን ታሪካዊው ባህታዊ አባ አምሃ ኢየሱስ ሰላማዊ ሰልፉን በሚገባ መርተውታል፡፡ አባ አምሃ ኢየሱስ ለሃይማኖታቸውና ለአገራቸው ሟች እና ዓለምን በቃኝ ያሉ ባሕታዊ ናቸው፡፡ በርካታ ዓመታትን ሕወሓት አስሮ አሰቃይቷቸው ከእስር የተፈቱት በቅርብ ጊዜ ነው፡፡ አዘዞ ላይ ፖሊስ የተወሰኑ ወጣቶችን አስሮ ከሕዝቡ ጋር ግጭት ለመፍጠር ሞክሮ ነበር፡፡ ሆኖም ጀግናው የዐማራ ሕዝብ በአንድነት የታሰሩትን ወጣቶች አስፈትቶ በሰላም ወደ ቤቱ ገብቷል፡፡
አቶ ዘመነ ምሕረት በአቶ ማሙሸት አማረ የሚመራው መኢአድ ምክትል ፕሬዝዳንት ከማክሰኝት እስከ ጎንደር በእግራቸው 40 ኪሎ ሜትር ያክል ከተጓዙ በኋላ ጎንደር እንዳይገቡ ተከልክለዋል፡፡
ከደብረ ታቦር ከዐሥር በላይ የህዝብ ማመላለሻ አውቶቡስ ለሰልፉ የሚሔዱ ሰዎችን አገልግሎት ሰጥቷል፡፡

2. ምዕራብ በለሳ አርባያ፡- ትናንት ምሽት በግጥም የወልቃይት ጠገዴን ዐማራነት እንዲሁም የወያኔ መንግሥት በዐማራ ሕዝብ ላይ የሚያደርሰውን በደል በተመለከተ ሲዘፍን ያመሸን ጎልማሳ ፖሊስ አስሮት አደረ፡፡ ዛሬ ከአርባያ፣ ደንቀዝ፣ ጎሃላና አካባቢው የተሰባሰበው የበለሳ ዐማራ የታሠረውን ጎልማሳ አስፈትቶ በሰላማዊ ሰለፍ ወያኔንና የትግራይን ተስፋፊነት ሲያወግዝ ውሏል፡፡ ከእኩለ ቀን በኋላ ሰልፉ ተበትኗል፡፡ ከአምሳ ሺህ በላይ ሰው ተሳትፎበታል፡፡

3. ጎንደር ዙሪያ ማክሰኝት፣ ከጎንደር 40 ኪሎ ሜትር በምትገኘው የማክሰኝት ከተማ ዛሬ ከሰዓት በኋላ ወጣቶች ለሰልፍ ወጥተው ነበር፡፡ ወያኔ ሌባ ነው፤ ዐማራ አሸባሪ አይደለም የሚሉ መፈክሮች አሰምተዋል፡፡ የፖሊስ አባላት ሰልፉን ለመበተን ጥረት አድርገው ነበር፤ ሆኖም ወጣቶች የሚፈለገውን መልእክተ አሰምተው መርሀ ግብራቸውን በሚገባ መልኩ አጠናቀዋል፡፡

4. ምዕራብ እስቴ፣ መካነየሱስ፡ ከጉና ተራራ ሥር የደንሳ አምባን ተንተርሳ የከተመችው የመካነ ኢየሱስ ከተማ ዛሬ ከእኩለ ቀን ጀምሮ በሰላማዊ ሰልፍ እየተናጠች ትገኛለች፡፡ እንደ መረጃ አቀባዮቻችን ሰልፉ ከሰዓት በኋላ በአካባቢው ያለው ገበሬ ሁሉ እንደተቀላቀለው ለማወቅ ተችሏል፡፡


በገደብ አሳሳ የመንግስት መስሪያ ቤቶች ወደሙ |ሰልፈኞች የውጭ ጉዳይ ሚ/ር ደኤታ መኖሪያ ቤትን አቃጠሉ

$
0
0

Gadab asasa 2 Gadab asasa gedeb asasa2

(ዘ-ሐበሻ) በኦሮሚያ የተለያዩ ከተሞች የተጀመረው ሕዝባዊ አመጽ እንደቀጠለ ነው:: ሕዝብ በመንግስት እና በመንግስት ደጋፊዎች ንብረት ላይ የበቀል እርምጃውን እየወሰደ መሆኑም ተሰምቷል::

ምዕራብ አርሲ በገደብ አሳሳ ቲጆ ዋቄንተራ ከተማ ዛሬ በተደረገ ተቃውሞ በአጋዚ ጥይት ወገኖቹ የተቆሉበት ሕዝብ ቁጣውን የመንግስት መስሪያ ቤቶችን ሰባብሮ በመግባት ሰነዶችን በመበታተንና በማቃጠል የበቀል እርምጃዎችን ወስዷል::

በዛሬው የገደብ አሰሳ ቲጂ ዋቄንተራ ከተማ ቤታቸው ከተቃጠለባቸው የ ስር ዓቱ ባለስልጣናት መካከል የውጭ ጉዳይ ሚኒስተር ደኤታው አቶ ዳዋኖ ከድር መኖሪያ ቤት እንደሚገኝበት ታውቋል:: እንደደረሰን መረጃ ከሆነ ተቃሟቸውን ሊገልጡ የወጡ ሰልፈኞች የምታስፈጀን አንተ ነህ በሚል የአቶ ዳዋኖ ከድርን መኖሪያ ቤት በ እሳት አንድደውታል::

“የትግራይ ህዝብ ምንም ነገር አልነበረውም ምንም አያጣም”

$
0
0

sebehat

በአስፋው ገዳሙ
ህወሓትና አጫፋሪዎችዋ ስለማንኛውም ህዝብ ደንታ እንደሌላቸው ያለፈው ታሪካቸው ቋሚ ምስክር ነው፡፡ህዝብ የሚበላው አጥቶ ይሰደታል….በአቋራጭ ለመበልፀግ ሰለሚፈልግ ነው ብለው ይወነጅሉታል፡፡እውነታው ግን የህወሓት አሽከርና ታማኝ ሎሌ ካልሆ በስተቀር ምንም ዓይነት ቤሳቢሰቲ እንደማያገኝ ይታወቃል፡፡የትግራይ ህዝብ ውሃ ጠማኝ ሲል፤ መልሳቸው ውሃ የተጠማኸው አንተብቻ አይደለህም የሚል ነው፡፡ራበኝ…ሰብአዊና ዲሞክራሲያዊ መብቶቼ ተቀማሁ፤ ለነፃነት ታግዬ ነፃነቴን ተገፈፍኩ ሲል ድሮውንስ መቼ ነፃ ነበርክና በሚል ደረቅ ጥፊ ያጮሉታል፡፡
1. የትግራይ ህዝብ ህወሓት ለርካሽ ፖለቲካዊ ትርፉ የጠራው ካልሆነ በስተቀር ህገመንግስታዊ መብቶቹን ለመጠየቅ ሰላማዊ ሰልፍ ማድረግ አይችልም፡፡ስለዚህ፣ የህወሓት ጨቋኝ ስርዓት ቢገረሰስ የሚቀርበት ነገር አየኖርም፡፡የሚቀርበት ቢኖር፣ ጭፈን ጎጠኝነት፣ ቤተሰባዊ አምባገነንነት፣ ኢፍትሐዊነት፣ በጠራራ ፀሐይ የሚከናወን ሙስና፣ ድህነትና ኋላ ቀርነት ብቻ ነው፡፡
2. በአሁኑ ሰዓት 19 ፐርሰንት የትግራይ ወጣቶች ስራ አጦች ናቸው፡፡ ያለ ድጋፍና ያለ መሪ የማይንቀሳቀሱ የህወሓት ሽማግሌዎች ግን ከነ ልጆቻቸው አምባሳደሮች ተደርገው ይሾማሉ፡፡ወይም የጠቅላይ ሚኒስተሩ ልዩ አማካሪ በሚል ሽፋን ሚሊዮኖች ይዝቃሉ፡፡ስለዚህ፣ የሽማግሌዎቹና ቤተሰቦቻቸው ስርዓት ቢደመሰስ የትግራይ ህዝብ ቅንጣት ታህል አያጣም፡፡
3. የትግራይ ህዝብ ለጋሽ ሃገሮች በሚመፀውቱት እርዳታ የሚኖር ህዝብ ነው፡፡እነዚህ ለጋሽ ሃገሮች ህወሓት የፈጠራቸው ስላልሆኑ ከህወሓት ጋር አብረው አይጠፉም፡፡እንዳውም እርዳታም የመሰሪ ፓለቲካቸው መጫወቻ መሆኑን ይቀራል፡፡እርዳታ ከፈለግ የህወሓት ሎሌ ሁን፣ ማዳበርያ ውሰድ፣ ቢርብህ ቢጠማህም በቀየህ ታጥፈህ ኑር ካልሆነ ግን መሬትህ ትነጠቃለህ…በወጣህበት ትቀራለህ የሚሉት የካድሬዎች ዛቻ ይቀርበታል፡፡የካድሬዎች መከበርያና መሆኑን ያበቃለታል፡፡
4. የትግራይ ህዝብ ህወሓትን ከ25 ዓመታት በላይ ተግሷታል…መክሯታል…መረረኝ ሰለቸኝ ብሎ ተማፅኗል፡፡ ሰሚ አላገኘም፡፡በአሁኑ ዘመን በአባይ ወልዱን ያልተሰላቸ ህሊና ያለው ትግራዋይ የለም፡፡አምና የተካሄደው የህወሓት ጉባኤ አባይን ያስወግድልናል የሚል ተስፋ የሰነቁ ብዙዎች ነበሩ፡፡ ህወሓት ግን ህዝቡ ስለሚለው ነገር አያገባትምና አባይ ባለበት ይቀጥላል…ምን ታመጣለህ የሚል መልእክት አስተላልፋለች፡፡በግሌ የፈለገው ቢሾምና ቢሻር ፋይዳ የለውም…ህወሓት የሚያመካት እንጂ ብቃት ያለው ሰው እንደማትሾም አውቃለሁና፡፡ስለዚህ ህወሓት ብትሰናበት የትግራይ ህዝብ የሚቀርበት…ለከት የሌለው ትእቢት፣ ንቀትና ምናለብኝነት ብቻ ነው፡፡
5. ህወሓት ወሬ አንጂ ተግባር አትወድም፡፡የተቃወሟትን ሁሉ ድምጥማጣቸውን ለማጥፋት ሲሆን ብቻ ነው ዋል እደር የማትለው፡፡እንደ መንግስት ግን እቅዶች ይታቀዳሉ እንጂ አይፈፀሙም፤ የመሰረት ድንጋዮች ይቀመጣሉ እንጂ ተጠናቅቀው ሲመረቁ አላየሁም፣ ዓመት ከዓመት ይሰበሰባሉ እንጂ ችግሮች አይፈቱም፡፡ስለዚህ፣ ህወሓቶች ቢሸኙ የትግራይ ህዝብ የሚቀርበት ወሬ ብቻ ነው፡፡የሚያጣው ስብሰባ ስብሰባ ስብሰባ … ብቻ ነው፡፡
6. ከህወሓት ባለስልጣኖች ጋራ በመሞዳሞድ የበለፀጉ ጥቂት ከበርቴዎች( ህወሓቶች ልማታዊ ባለሃብቶች ይሏቸዋል) አሉ ፤ የማይካድ እውነታ ነው፡፡በህወሓት ባለስልጣናት የሚመሩና የባለስልጣናቱና ቤተሰቦቻቸው ኪስ የሚያደልቡ ድርጅቶች አሉ፤ ለስሙ የትግራይ ህዝብ ናቸው… የትእምት ኩባንያዎች፡፡ለትግራይ ህዝብ ምን ፈየዱለት? ምንም! እንዳውም የህወሓት ካድሬ ወይም የካድሬዎች ቤተሰብ ካልሆነ በስተቀር እንደ ዜጋ በእነዚህ ድርጅቶች መቀጠር እንኳን አይችልም፡፡ቢሆንም ግን እነዚህ ድርጅቶች ከጉለት ችርቻሮ እስከ አስመጪና ላኪነት፣ ከጥሬ እቃ አቅራቢነት እስከ ፋብሪካው፣ ከብድር አከፋፋይነት እስከ ማዳበርያ አስመጪነት፣ ከመንገድ እስከ ህዝብ አመላላሽነት … በሃገሪቱ ባልታየ ታሪፍ ሙሉ በሙሉ ተቆጣጥረውታል፡፡ ስለዚህ፣ ህወሓትና ኢፍትሓዊ ድርጅቶቿ ከትግራይ ህዝብ ጫንቃ ቢወርዱ ከመዥገር እንደተላቀቀ እፎፎፎፎ ይላል እንጂ ቅንጣት አይቆጨውም፡፡
7. የትግራይ ዳር ድምበሮች… በተለይ ኤርትራና ሱዳን የሚያዋስኑ ድምበሮች የወታደር ምሽጎች ናቸው፡፡ቢሆንም ግን የትግራይ ህዝብ በሻዕብያ ወታደሮች መታፈኑን አልቀረም… በአማፂ ድርጅቶች በሚጠመዱ ፈንጆች ህይወቱን ማጣቱን አልቀረም…በህገ ወጥ የሰው ልጅ አመላላሾችና ነጋዴዎች እየታፈነ መወሰዱን አልቀረም፡፡ በአጠቃላይ የሚወራው ልማት ተቋዳሽ እንዳልሆነው ሁሉ ሰላምና ድህንነቱም አልተጠበቀም፡፡ስለዚህ በህወሓት አለመኖር የሚያጣው ነገር አይኖርም፡፡

8. የትግራይ ህዝብ ሓሳቡን የሚገልፅበት ነፃ የመገናኛ አውታር የለውም፣ ሰላማዊ ሰልፍ የማድረግ መብት የለውም፣ ከህወሓት በስተቀር ሌላ ፓርቲ መምረጥ፣ በግሉም መመረጥ አይችልም፣ በሃገሩ እኩል ተጠቃሚ አይደለም፣ የፍትሕ ያለህ እያለ ከጮኸ 20 ዓመታት አልፏል …በአጠቃላይ ስለዲሞክራሲ ሲደሰኮር እንጂ የዲሞክራሲ ሽታ አላሸተተም፡፡
በስሙ ተነገደበት እንጂ ነግዶ አላተረፈም፤ በለፀጋችሁበት እንጂ አልበለፀገም፣ ጥራት ያለው ህክምና ይሁን ጥራት ያለው ትምሀርት አላየም፡፡ ልጆቻችሁ ባማታስተምሩባቸው ትምህርት ቤቶች ልጆቹን ያስተምራል፤ ራሳችሁ በማትታከሙባቸው ሆስፒታሎችና ጤና ጣብያዎች ይታከማል፡፡
ልጆቻችሁ ውጪ ሃገር ተስተምራላችሁ…ስለትምህርት ጥራት አይገዳችሁም! ስትታመሙ ውጪ ሃገር በዶላር ከፍላችሁ ትታከማላችሁና ስለጤና ተቋማት ጥራት አያሳስባችሁም!
ሰለዚህ፣ እናንተ ከህወሓት ጋራ በመሞዳሞድ ሳይገባችሁ ልዩ ተጠቃሚዎች የሆናችሁ ልማታዊ ጋዜጠኞች፣ ልማታዊ ምሁራን፣ ልማታዊ ባለሃብቶችና ዘመናይ ባለስልጣኖች ሆይ…ህወሓት ስላለች የትግራይ ህዝብ ያገኘው ነገር የለም፤ ህወሓት ከሌለችም የሚያጣው ነገር የለምና የአዞ እንባችሁን ወደዛው!!!”

ተስማምቻለው።

ምዕራፍ አንድ!

$
0
0

ምንም እንኳ ሰላማዊ ሰልፍ ለማድረግ ማሳወቅ እንጅ ፈቃድ መጠየቅ ሕጋዊነት ያለው አሠራር ባይሆንም ይህ ታላቅ ሰልፍ የተደረገው በወያኔ ፈቃድ ሆኖ ቢሆን ኖሮ ምንም ሊሰማኝ የሚችል ነገር ባልነበረ ነበር፡፡

amhara
ነገር ግን የጎንደር ሕዝብ ንቅል ብሎ በመውጣት ይሄንን ታላቅ ታሪካዊ ሰልፍ ያደረገው ወያኔ ይሄንን ሰልፍ ሕገ ወጥና ፈቃድ ያልተሰጠው ብሎ ባወጀበት ሁኔታና የተቃውሞ ሰልፉን ለማስቀረት ለማክሸፍ ለማሰናከል ከባባድ ማስፈራሪያዎችን ጨምሮ ሌሎች የአፈና እርምጃዎቹንና ስልቶቹን አሟጦ ተጠቅሞ እያለ ሕዝቡ ለዚህ የወያኔ አንባገነናዊ የአፈና እርምጃና ማስፈራሪያ ቅንጣት ታክል ሳይበገር ነቅሎ በመውጣት ለአንባገነኑ የወያኔ አገዛዝ ግፍና በደሎቹ ያለውን መራር ተቃውሞ የገለጸበት፣ ብሶቱን ያሰማበት፣ በደሉን ያስታወቀበት፣  ብሔራዊ ስሜቱን ያስተጋባበት፣ ባለአደራነቱን ያረጋገጠበት፣ የበቃኝ መልዕክቱን ያስተላለፈበት ታላቅ ሕዝባዊ የተቃውሞ ሰልፍ በመሆኑ ኩራት የሚሞላ ጀብድ ነው፡፡

ነገር ግን ይህ ልናደርገው ከሚገቡን እርምጃዎች አንዱ እንጅ በራሱ የመጨረሻ ግብ ባለመሆኑ በዚህ ስኬት ሳንዘናጋና ወያኔ በዚህ ታላቅ ሕዝባዊ የተቃውሞ ሰልፍ እንዲፈጽም፣ እንዲያሟላ፣ እንዲያስተካክል ለተላለፉለት ጠንካራ ሕዝባዊ መልዕክቶችና ጥያቄዎች ጆሮ ሰጥቶ ይስተካከላል ያሟላል ይፈጽማል ተብሎ ስለማይታሰብ ስለማይጠበቅና ከነ ችግሮቹ በደሎቹና ግፎቹ ከመክሰም ከመጥፋት በስተቀር የመስተካከል የማሟላት የመፈጸም ዕድል ፈጽሞ ስለሌለው ይህን አንባገነናዊ አረመኔ አገዛዝ በተቻለን ፍጥነት ከስሩ ነቅለን ለመጣል የሚያስችሉንን ቆራጥ እርምጃዎች በሙሉ አከታትለን ማድረግ የግድ ይጠበቅብናል፡፡

ይህን የተቀደሰ ብሔራዊ ተልዕኮ ለስኬት ከማብቃት አኳያ እስከ አሁን ይህ እየተደረገ ያለውን የተቃውሞ እንቅስቃሴ ያልተቀላቀልከው የተቀረኸው የኢትዮጵያ ሕዝብም በዝምታ እንድትመለከት ሊያደርግህ የሚገባ አንዳችም ምክንያት የለምና በዚህ አንገብጋቢ የሞት ሽረት የትግል ወቅት ዝምታ የሀገር ክህደት ነውና ጊዜ የለም በቶሎ ተቀላቀል!!!

በተለይም አዲስ አበባ! እንዴት ነው አዲስ አበባ??? ነቃ በይ እንጅ!!! ይሄው አዲሱን ምእራፍ ጎንደር ባርካ ጀምራልሻለች አንች ተቀብለሽ በአስደናቂ አጨራረስ ቤተመንግሥቱን ከተባይ አጽድተሽ ግሩም ስኬት እንደምታስመዘግቢ ተስፋ አደርጋለሁ!

እንዴት ነው ታዲያ ነቃ ነቃ አዲስ አበባ! ነቃ ነቃ መላው ኢትዮጵያ!
ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!!! ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር!!!
ሠዓሊ አምሳሉ ገ/ኪዳን አርጋው
amsalugkidan@gmail.com

የጎንደሩ ተቃውሞ ሰልፍ የ5 ደቂቃ ቪዲዮ

ጎንደር፡- ሕዝብ ተከፍቶም –ተገፍቶም አይችልም

$
0
0
ስዩም ተሾመ

ስዩም ተሾመ

ከስዩም ተሾመ

ዛሬ በጎንደር ከተማ ስለተካሄደው ሰላማዊ ሰልፍ ዓላማ፣ ግብ፣ መልዕክቶች፣…ወዘተ ስለመሳሰሉት ጉዳዮች በማህበራዊ ድረገፆችና በዲያስፖራው ሚዲያዊች በሰፊው እንደሚዘገብ እገምታለሁ። በእነዚህ ጉዳዩዮች ዙሪያ በቂ መረጃ ይቀርባል። ስለዚህ፣ የእኔ ትኩረት “ከዛሬው ሰላማዊ ሰልፍ ምን እንማራለን?” በሚለው ነጥብ ላይ ነው። በተለይ ደግሞ የክልልና የፌዴራል መንግስታት ምን መማር አለባቸው የሚለውን እንመለከታለን።

የአማራ ክልላዊ መንግስት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ፅ/ቤት ትላንት በሰጠው መግለጫ “በጎንደርም ሆነ በሌሎች ከተሞች የተጠየቀም የተፈቀደም ሰላማዊ ሰልፍ የለም” ብሎ የነበር፡፡ ዛሬ ደግሞ “በጎንደር ከተማ የተካሄደው ሰለማዊ ሰልፍ ምንም እንኳን በመንግስት የተፈቀደ ባሆንም ሰላማዊ ነበር…” እያለ ይገኛል።

በእርግጥ ይህ የብአዴን/ኢህአዴግ መግለጫ እናቴን ነበር ያስታወሰኝ። ልጅ እያለሁ፣ በተለይ ደግሞ ከእናቴ አጠገብ ስሆን ፈርዶብኝ የሆነ ነገር አጠፋለሁ፡፡ ታዲያ ይቺ እናቴ “እስኪ ትንፍሽ በል…ዋ! ዝም…ዝም በል…” እየለች ነበር የምተገርፈኝ፡፡ መግረፏ ሳያንሰኝ “ዝም በል” ማለቷ የባሰ ያስጨንቀኝ ነበር፡፡ ዝም እንዳልል ምቷ ሰለሚያመኝ አለቅሳለሁ … ሳለቅስ ደግሞ “ዝም በል” ብላ ከዱላው ትጨምርልኛለች፡፡ መጨረሻ ላይ ሲመረኝ ብንን ብዬ ከአጠገቧ በሩጫ አመልጣለሁ፡፡ ዛሬ የጎንደር ህዝብ ልክ እንደ እኔ በምሬት ሮጦ ወደ አደባባይ የወጣ ይመስለኛል፡፡

Gonder6

በተለምዶ “ሰው ፖለቲካዊ እንስሳ ነው” ይባላል። ይህ አባባል ለምን እንደሚባል አይገባኝም ነበር። ትርጉሙ የገባኝ “Aristotle” የተባለው የግሪክ ፈላስፋ “Politics” በሚለው መፅሃፉ ስለዚህ አባባል የሰጠውን ትንታኔ ካነበብኩ በኋላ ነው። እንደሱ አገላለፅ፣ ሰው ከሌሎች እንስሳት በተለየ ሕመም እና ደስታን (Pain and Pleasure) በቋንቋ መግለፅ ይችላል፡፡ የቋንቋ ችሎታውን በመጠቀም መከፋቱንና ደስታውን፣ ድጋፍና እና አቤቱታውን በቀጥታ በንግግር፣ በፅሁፍ ወይም በሰልፍ መግለፅ ይችላል።

በመሆኑም፣ እያንዳንዱ ግለሰብ በግል እና በቡድን የሚያደርገው ማህበራዊ ግንኙነት በዚህ ተፈጥሯዊ ባህሪ ላይ የተመሰረተ መሆኑን በመጥቀስ፣ “ሰው ፖለቲካዊ እንስሳ ነው!” (Man is a political animal) ይላል “Aristotle”። አባባሉ “ሰው ፖለቲካዊ እንስሳ ነው” ሲባል በአንድ ነገር ላይ የተሰማውን ጥሩም ይሁን መጥፎ ስሜት በግል ወይም በቡድን በቃል ንግግር፣ በወረቀት ፅሁፍ ወይም እንደ ዛሬው በአደባባይ ሰልፍ የመግለፅ ተፈጥሯዊ ባህሪ እንዳለው ያሳያል።

በአጠቃላይ፣ ሰው በአንድ ነገር ላይ የተለያየ አመለካከት መያዙና ሃሳቡን መግለፁ ተፈጥሯዊ መለያ ባህሪው ነው። ለዚህ ነው ዓለም-አቀፍ ድንጋጌዎችም ሆኑ ሀገር-አቀፍ ሕጎች ሰው ያለማንም ጣልቃ-ገብነት የመሰለውን አመለካከት መያዝና ሃሳቡን የመግለፅ ነፃነት እንዳለው የሚደነግጉት። ምክንያቱም፣ ይህ የሰው-ልጅ ተፈጥሯዊ ባህሪ እንጂ በሌላ አካል ፍቃድና ይሁንታ የሚሰጥ አይደለም።

የኢፊዴሪ ሕገ-መንግስት አንቀፅ 30 ለዚህ ጥሩ ማሣያ ነው።

“ማንኛውም ሰው ከሌሎች ጋር በመሆን ማሣሪያ ሳይዝ በሰላም የመሰብሰብ፣ ሰላማዊ ሰልፍ የማድረግ ነፃነትና አቤቱታ የማቅረብ መብት አለው። ከቤት ውጪ የሚደረጉ ስብሰባዎችና ሰላማዊ ሰልፎች በሚንቀሳቀሱባቸው ቦታዎች በሕዝብ እንቅስቃሴ ላይ ችግር እንዳይፈጥሩ ለማድረግ…አግባብ ያላቸው ስርዓቶች ሊደነገጉ ይችላሉ።”

ከላይ በጥቅሱ ውስጥ እንደተጠቀሰው፣ በሕዝብ እንቅስቃሴ ላይ ችግር እንዳይፈጠር በሚል የሚወጣ ማንኛውም ዓይነት ስርዓት ከሕገ-መንግስቱ መሰረታዊ መርህ ጋር የሚጋጭ መሆን የለበትም። ሰላማዊ ሰልፉ በሚካሄድበት ቦታ የሚመለከተውን የመንግስት አካል ከማሳወቅ በስተቀር ሌላ ፍቃድ መጠየቅም ሆነ መጠበቅ የለበትም። ሰላማዊ ሰልፍ ለማድረግ የሚካሄድበትን ቦታና ግዜን ከማሳወቅ ሌላ ፍቃድ የሚጠይቅ አሰራር ሊኖርም አይችልም። እንዲህ ያለ አሰራር ቢኖርም እንኳን ሕገ-መንግስቱን የሚጥስ ስለሆነ በሕዝብ ዘንድ ተቀባይነት የለውም።

ከዚህ አንፃር፣ የአማራ ክልል መንግስት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ፅ/ቤት በጎንደር ከተማ ለሚደረገው ሰለማዊ ሰልፍ “ፍቃድ አልሰጠሁም” ሲል ያወጣው መግለጫ በራሱ በቂ ማስረጃ ነው። ምክንያቱም፣ በሕገ-መንግስቱ መሰረት በሰላማዊ ሰልፍ ተቃውሞና አቤቱታን ለመግለፅ የሚጠበቀው ማሳወቅ ብቻ ነው። የክልሉ የመንግስት ኮሚዩኒኬሽን ፅ/ቤት “በጎንደር ከተማ ነገ ለሚደረገው ሰላማዊ ሰልፍ ፍቃድ አልሰጠሁም” በማለት የሰጠው መግለጫ በራሱ ሰላማዊ ሰልፉ እንዲካሄድ ከመፍቀድ ጋር እኩልና አንድ ነው። በመሰረቱ ከሕዝቡ የሚጠበቀው ማሰወቅ ብቻ ስለሆነ የፅ/ቤቱ መግለጫ የክልሉ መንግስት ማወቅ ያለበትን አውቋል ማለት ነው። በአጠቃላይ፣ “ሰላማዊ ሰልፍ እንዲካሄድ አልፈቀድኩም” ማለት በራሱ “ፈቅጄያለሁ” እንደማለት ነው።

መንግስት ማለት የጋራ ሰላምና ደህንነታችንን እንዲያስከብርልን በሚል ውክልና የተሰጠው አካል ነው። በውላችን (ሕገ-መንግስት) መሰረት ራስን-በራስ የማስተዳደር ስልጣናችንን እና የሀብታችንን አሳልፈን ሰጠነው። ሕዝብ የሰጠውን ስልጣንና አቅም ተጠቅሞ የብዙሃኑን መብትና ጥቅም ከማረጋገጥ ይልቅ የህዘቡን መብት ወደጎን ትቶ የራሱን ጥቅም አስቀደመ።

በህዝብ ፍቃድ ላይ የተመሰረተ መንግስት ያለእሱ ፍቃድ መናገር አትችሉም ሲል፣ ሕዝብ ወካይ፣ መንግስት ተወካይ መሆኑ ቀርቶ ነገሩ የተገላቢጦሽ ሆነ። መንግስት በተግባር ማስከፋቱ ሳያንስ፣ ህዝብ “ከፍቶኛልና አቤቱታዬን አደባባይ ወጥቼ ላሰማ” ሲል ያለእኔ ፍቃድ አይሆንም ይላል። ሲጀመር ሕዝቡን ያስከፋው እኮ መንግስት ነው፡፡ ያስከፋውን ሕዝብ አቤቱታውን እንዲገልፅ ፈቃጅ መሆን የሚሻውም መንግስት ነው። አንዴት ሕዝብን አስከፍቶ አቤቱታውን አልሰማም ይላል? ታዲያ ሕዝብን አስከፍቶም-ገፍቶም ይቻላል እንዴ?

በእርግጥ ዛሬ በጎንደር ከተማ የታየው ሰላማዊ ሰልፍ “ሕዝብን አስከፍቶም፣ ገፍቶም” መቀጠል እንደማይቻል ነው። በመጀመሪያ፣ የሚገፋውን አካል ገፍትሮ በመውጣት መከፋቱንና ብሶቱን ይገልፃል። በቀጣይ ሲመጣ ግን አስከፍቶ የሚገፋውን መንግስት ገፍትሮ ይጥለዋል። በኃላ ላይ ከመገፍተር አሁን መማር የሚበጅ ይመስለኛል።

Viewing all 15006 articles
Browse latest View live