Quantcast
Channel: Ethiopian News | ዘ-ሐበሻ | Latest News Provider | News For All
Viewing all 15006 articles
Browse latest View live

Hiber Radio: “በኢትዮጵያ ስም እንማማላለን እንጂ አንተባበርም”–ዶ/ር መረራ ጉዲና (ቃለ ምልልስ Audio)

0
0

merara gudinaህብር ሬዲዮ ከዶ/ር መረራ ጊዲና የመድረክ እና የኦሮሞ ፌደራላዊ ኮንፈረንስ የወቅቱ ሊቀመንበር ጋር የተደረገ ወቅታዊ ቃለ መጠይቅ

ዶ/ር መረራ ጊዲና ስለ ተቃዋሚዎች የትብብር ጥያቄ፣ በወቅቱ የሰላማዊ ሰልፍ እንቅስቃሴ የት ድረስ መሄድ እንደሚቻል፣ በገዢው ፓርቲ የኮንደሚኒየም ተመዝገቡ ዘመቻ፣ በውጭ ያለው በአገሩ ለውጥ እንዲመጣ የሚደግፈው ሀይል እውን ተገቢውን ድጋፍ ያደርጋል? ተቃዋሚዎችስ የሚገባቸውን ያህል እየተንቀሳቀሱ ነው? ስለ አዲሱ > መጽሐፋቸው ምን ይላሉ? ለምድነው የኦሮሞ ተወላጅ ኢትዮጵያውያን በውጭ አገር ከሌሎች ወገኖቻቸው ጋር ተሰልፈው የማይታገሉት? የሙስሊሙን ሰላማዊ እንቅስቃሴን አስመልክቶና በሌሎችም ጥያቄዎች ላይ አወያይተናቸዋል። ለአጭር ጊዜ ቆይታ በመጡበት አግኝተን ለአቀረብንላቸው ጥያቄ በመቀበል ፈቃደኛ በመሆናቸው በህብር ሬዲዮ አድማጮች ስም እናመሰግናለን:-


ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ እና አንዳርጋቸው ጽጌ ወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ ከሕዝብ ጋር ሊወያዩ ነው

0
0

(ዘ-ሐበሻ) የግንቦት 7 ንቅናቄ አመራር የሆኑት ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ እና አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ እሁድ ሴፕቴምበር 22 ቀን 2003 በዋሽንግተን ዲሲ/ ቨርጂኒያ በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ለሕብረተሰቡ ገለጻ ለማድረግ ሕዝባዊ ስብሰባ መጥራታቸውን የመርሃ ግብሩ አዘጋጆች ለዘ-ሐበሻ በላኩት በራሪ ወረቀት አስታወቁ። “የወቅቱ የኢትዮጵያ ተጨባጭ ሁኔታና ለነፃነትና ለዴሞክራሲ የሚደረገው ትግል ላት ገለጻ ይደረጋል” በሚል በአርሊንግተን ቨርጂኒያ ከቀኑ 2 ሰዓት ጀምሮ የተጠራው ይኸው ሕዝባዊ የውይይት መድረክ ሰፊ የጥያቄና መልስ ክፍል ስለሚኖረው ማንኛውም ኢትዮጵያዊና ኢትዮጵያን ወዳጅ በመገኘት እንዲሳተፍ አዘጋጆቹ ጥሪያቸውን አቅርበዋል። ለዚህ ሕዝባዊ ውይይት መድረክ የመጥሪያ በራሪ ወረቀት የሚከተለው ነው።

Dr berehanu nega

የኢትዮጵያውያን ባህልና የጋብቻ ቅድስና – (ተፈራ ድንበሩ)

0
0

ኢትዮጵያ ቅድስት መሆኗን የሚያሳዩ ማስረጃዎች፤
ኢትዮጵያ የሚለው ያገራችን መጠሪያ የተገኘው በካም ወገን ሴማዊ ከሆነውና ከነሙሴና አሮን በፊት ካህን ከነበረው መልከጼዴቅ ከሚባል ኢየሩሳሌምን ከመሠረተው ንጉሥ በተወለደውና ኢትዮጵ ከሚባል በኋላ ኢትዮጲስ ተብሎ የኢትዮጵያ ንጉሠነገሥት ከነበረ ሰው የመጣ ስያሜ መሆኑን የቤተክርስትያን መረጃዎች ያመለክታሉ (ፍቅሬ ቶሎሳ 1-10)። ኢትዮጵያውያን ከሁለቱ የኖህ ልጆች ካም (በኩሽ በኩል) እና ሴም (በአብርሃም በኩል ከእሥራኤላውያን ወገን) የተገኙና ተደባልቀው የተባዙ ዘሮች ሲሆኑ ለምሳሌም አፋር (ከ Ophir) የሴም ወገን ከሆነው ነገደ ዮቅጣን የመጣና በአፍሪካ ቀንድ ከጥንት ጀምሮ የነበረ ሕዝብ ሲሆን የአህጉሩ መጠሪያም ከዚሁ ቃል እንደተገኘ ይነገራል። በአርኪዎሎጂና አንትሮፖሎጂ ጥናት ከመረጋገጡ በፊት ሔሬዶተስና ዲዎዶረስ የተባሉ የጥንት የታሪከ ፀሐፊዎች የመጀመሪያው ሰው የኖረው በኢትዮጵያ እንደነበረ ጽፈዋል (Gates 68)። ኢትዮጵያውያን ዛሬ በቋንቋ ተለያይተው ይታዩ እንጅ፣ የካም፣ የሴም፤ የኦሞቲክና የኒሎቲክ ነገዶች ውሁድ የሆነ አንድነት አላቸው። በባህል ብቻ ሳይሆን በዘርም ተቀላቅለዋል። አሁን ባገራችን ከሚነገሩት ከ፹ በላይ ቋንቋዎቻችን ውስጥም ብዙዎቹ ከጥንቱ ግዕዝ፣ ከሳባ (ሱባ)፣ እብራይስጥ፣ ግሪክና ከሌሎች የሴምና የኩሽ እንዲሁም በአባይ ወንዝና ኦሞ ሐይቅ የተሰየሙ (ኒሎቲክ እና ኦሞቲክ ) አፍሪካዊ ቋንቋዎች ተገኝተውና ተቀያይጠው ትውልዶች እየበዙ ሲሄዱ በተጓዳኝ የተባዙ ናቸው።

መጽሐፍ ቅዱስ እንደሚያመለክተን ኢትዮጵያ በእግዚአብሄር ዘንድ ከፍተኛ የቅድስና ደረጃ አላት (መዝሙር ፷፰፤፴፩፣ ትንቢተ አሞጽ ፱፡፯)። አገራችን መንፈሳዊነት የሰፈነበት ባህል ያላት ስለሆነች ልዩነቶችን አቻችሎ አብሮ መኖርን፣ ለጋስነትን፣ መረዳዳትንና እንግዳ ተቀባይነትን አዋህዳ ለቤተሰብም ከፍተኛ ክብር በመስጠት የኖረች የጥንት አገር ነች። ሆኖም ትውልድ እየበዛ ሲሄድ ይህች ምድራዊ ገነት የሆነች አገር በየቦታው የተሟላ የተፈጥሮ ሀብትና የአየር ንብረት ስላላት ብዙዎች ሕዝቦቿ በተለያዩ አካባቢዎች በወንዝ፣ ተራራ፣ ወዘተ ተካለውና ራሳቸውን ችለው ለረጅም ዘመናት ሲኖሩ በቋንቋዎቻቸውም እንደዚሁ ተለያይተው ዛሬ የሚታየውን የብሔር-ብሔረሰብ ሰያሜዎች ዝርዝር ሊያስከትል ችሏል (ተፈራ ድንበሩ 59-60) ።
eth church cry
በመዝሙር ፷፰፡፴፩ ላይ “ኢትዮጵያ ታበፅሕ እደዊኃ ሀበ እግዚአብሔር” የተባለችበትም ያለምክንያት አይደለም፤ ከእግዚአብሔር በሲና ተራራ ሕገ-ኦሪትን የተቀበለው ሙሴ የተመላለሰባት፣ ክርስቶስ ከእናቱ ከቅድስት ድንግል ማርያም ጋር በሕፃንነቱ ተሰዶ የሄደባት አገር በመሆኗ ኢትየጵያ ለቅድስት ድንግል ማርያም አሥራት እንደተሰጠችና በሷ አማላጅነት የመዳን ተስፋ እንደተሰጠን ቅዱሳት መጻሕፍት ይናገራሉ። በ፬ኛው መቶ ክፍለ ዘመን በቅዱስ ፍሬምናጦስ/አባሰላማ/ አማካይነት ክርስትና በመንግሥት ደረጃ ቢታወጅም ከዚያ በፊት ሐዋርያው ቅዱስ ማቴዎስ ወንጌልን ያስተማረበት አገር ነበረች፤ ቅዱስ ፊልጶስ ያጠመቀው የቤተመንግሥት ሹም ወደ ኢየሩሳሌም ለአምልኮት መሄድ ቀደም ሲል ኢትዮጵያውያን ከኢየሩሳሌም ጋር የነበራቸውን ሃይማኖታዊ ትሥሥር ያመለክታል (የሐዋርያት ሥራ ፰፡፳፮)። ክርስትና ቀድሞ ከገባባቸው አገሮች አንዷ ኢትየጵያ ስለሆነች ኦሪትንና ሐዲስን አጣምራ የቆየች ብቸኛ አገር ነች። እንዲሁም ፳፻/ ሁለት ሺ/ ዓመታት ከክርስቶስ ልደት በፊት በሥነጽሐፍ ዕድሜው ተወዳዳሪ ያልተገኘለት የግዕዝ ቋንቋችን በጽሐፍ ላይ የነበረ የመንግሥት መገልገያ ቋንቋ ሲሆን መጽሐፍ ቅዱስ መጀመሪያ ከተጻፈባቸው በጣት ከሚቆጠሩ — እብራይስጥ፤ አርማይክ፣ ፅርእ/ግሪክ/፣ ሲራይክ፣ ኮፕቲክ እና ከላቲን ቋንቋ በፊት የነበረ የአገራችን ትልቅ ሰነድ መሆኑ ሊያኮራን ይገባል። በቀደምት ሥነጥበብ ሙያ የሚታወቁት እነሼክስፔር፣ ሚካኤል አንጀሎና ላዎናርድ ዳቪንሲ ከመፈጠራቸው ከ፩ ሺ ዓመት በፊት ዓለም በጭለማ ውስጥ በነበረበት በ፮ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ታላቁ የቤተክርስትያናችን የዜማ አባት ቅዱስ ያሬድ ድጓ፣ ጾመድጓ፣ ምእራፍ፣ ዝማሬና መዋሴትን ደርሶ የግዕዝ፣ እዝልና አራራይን ቅኝት ለዓለም አበርክቷል።
አገራችን የብዙ ጻድቃንና ሰማዕታት አገር ነች፤ ለምሳሌ በ፲፭ኛው መቶ ክፍለ ዘመን የነበረችው ክርስቶስ ሰምራ የኃጢአት ምንጭ የሆነው ሰይጣን ከአምላካችን ይቅርታ ተደርጎለት የሰው ልጅ ሁሉ ሥርየት እንዲያገኝ ቀንና ሌሊት በመፀለይ የቅድስና ሥራ የሠራችና ሌሎች እንደ አቡነ ገብረመንፈስቅዱስ፣ አቡነ ተክለሃይማኖት፣ አቡነ አረጋዊ፣ አባ ሣሙኤል ዘዋልድባ፣… ወዘተ ያሉ የቅድስና ገድሎቻቸው በቤተክርስትያን የሚታወቅላቸው ታላላቅ መንፈሳውያን አገር ነች። እንዲሁም ኢየሱስ ክርስቶስ በቤተልሔም እንደሚወለድ አወቀው ለክብሩ የሚገባውን ስጦታዎች ይዘው በኮከብ እየተመሩ ወደ ኢየሩሳሌም ከሔዱት ሰባሰገል ከሚባሉ አዋቂ ሰዎች መካከል ኢትዮጵያውያን ነበሩበት። ኢትዮጵያ ኦሪትን ከሐዲስ ኪዳን ጋር አስማምታ ፈሪሀ እግዚአብሄር ያደረበትንና የሰውን ልጅ አክብሮ፣ መብቶቹን ጠብቆ ማኅበራዊ አኗኗርን አዋህዶ የተሟላ ባህል ካላቸው ቀደምት አገሮች ውስጥ የሚተካከላት እንደሌለ ያሁኑ ልጆቿ ጠንቅቀው ያውቃሉ?

የሮማው መሪ ጁሊየስ ቄሣርና የአይሁድ መሪ ሄሮድስ ሥልጣናቸውን ለማቆየት የተወለደ ሕፃን ሁሉ ሲገድሉ ኢትዮጵያ ሰብአዊነትን በሚከተሉ የጥበብ ሰዎች ትመራ ነበር (ፍቅሬ ቶሎሳ 29-30)። እንደ ፈረንሳይ፣ ጀርመን፣ እንግሊዝ የመሳሰሉ የአውሮጳ አገሮች ማንበብ መጻፍ በማያውቁባቸውና ያልሠለጠኑ (barbarians) በነበሩባቸው ዘመናት አገራችን በራሷ ፊደል በተጻፈ ሕግና በመንግሥት ትመራ ነበር። በአውሮፓ ሰዎች በባህር ላይ ዘረፋ (piracy) ሲተዳደሩ በነበሩ ጊዜ ኢትዮጵያ ሕግና ሥርዓት የሰፈነባት አገር ነበረች። ሰብአዊ መብት በሌላው ዓለም እየተጣሰ ሰላማዊ ሕዝቦች ሲበደሉ ያገራችን መሪዎች ታድገዋቸዋል። የአይሁድ አክራሪዎች በአረቢያ ናግራን፣ በግብፅ የእስልምና አክራሪዎች በክርስትያኖች ላይ የፈጸሙትን የሰብአዊ መብት ጥሰት ተከላክለዋል፤ ሆኖም በዓለም ላይ በተፈጸመው የሃይማኖት ጦርነት ውስጥ ኢትዮጵያ አልተሳተፈችም። የአገራችን መሪዎች ከ፪፻ በላይ የእስልምና እምነት ተከታዮችን በእምነታቸው ምክንያት ለሕይወታቸው ሲሸሹ በስደት እኤአ በ፮፻፲፫ እና ፮፻፲፭ ዓም ተቀብለው አስተናግደዋቸዋል። ስደተኞቹን እንዲመልሱ የአረቢያው መሪ አቡ ሱፊያን በኃይል ለመጠቀም ቢዝትም የኢትዮጵያ ንጉስ አርማህ (አል አስማሃ ወይም ነጋሽም ይባሉ ነበር) የሚመጣውን ኃይል በኃይል መክቶ ለመመለስ በመወሰን የስደተኞቹን መብት በማስከበር በዓለም የመጀመሪያው መሪ ነበሩ። በዚህ የተነሣ ንጉሡን ነጃሽ በማለት በስማቸው መስጊድ አሠርተው አክብረዋቸዋል፤ ሆኖም አንዳንድ የአሁኑ እስልምና ሃይማኖት ፀሐፊዎች ለክብራቸው የተሠራላቸውን መስጊድ እንደማስረጃ በመውሰድ ንጉሥ አርማህን እስላምናን ተቀብለዋል እስከማለት ደርሰዋል።

ኢትዮጵያ በተለያዩ ጊዜያት በእንግድነት ወይም በጥገኝነት መጥተው በሰላም የሚኖሩ የማናቸውንም የሕዝብ ወገኖች ተቀብላ በማስተናገድ የታወቀች ነች። ማናቸውንም ሃይማኖት የሚከተሉ ኢትዮጵያውያን ሰው በመግደል ጽድቅ አለ ብለው ሳይሆን በመፈቃቀር የሚያምኑ ሲሆን፤ የእስልምና፣ የአይሁድና የክርስትና እምነት ተከታዮች ተከባብረው በሰላም የሚኖሩባት አገር ነች። ኢትዮጵያዊ ስደተኞችን መንገድ በመምራት የምትታወቅ ሲሆን፣ ዛሬ እንደ ሲናይ ባሉ የአረብ በረሀዎች ስደተኞች በእንግድነታቸው መንገድ ሲጠይቁ በአጻፋው በአንድ በኩል ሃይማኖት አለን ብለው በሚመጻደቁ በሌላ በኩል ደግሞ ነፍሰገዳይ በሆኑ ሰዎች ንብረታቸው ተዘርፎ የሚሰጡት ሲያጡ የሰውነት ሕዋሳቶቻቸው ተቆራርጦ የሚሸጥበት ዓይነት ክስተት በኦጋዴን፣ አውሳ፣ ቤኒሻንጉል ጉሙዝ፣ ትግራይ፣ አፋር… ወዘተ በማናቸውም የኢትዮጵያ ክፍለ ሀገር ባላገር ዘንድ እንዲህ ያለ ድርጊት አስነዋሪ ነው።
ኢትዮጵያ ዲፕሎማሲን በማስተማር ቀደምት ከሆኑ አገሮች አንዷ ስትሆን ንግሥት ሳባ ለንጉሥ ሰሎሞን ባበረከተችው ስጦታ በእሥራኤልና ኢትዮጵያ መካከል አንድነት አንዲፈጠር ከማድረጉም በላይ ከንጉሥ ሰሎሞን በተወለደውና በኋላም በኢትዮጵያ በነገሠው ቀዳማዊ ምንሊክ አማካይነት የመጀመሪያው ጽላት ወደ አገራችን ገብቶ ይገኛል። ክርስቶስ የተሰቀለበት ግማደ-መስቀልም እንደዚሁ በአገራችን በግሸን ገዳም የሚገኝ ሲሆን በአገራችን የተፈጸሙ አያሌ መንፈሳዊ ገድሎችን ከቤተክርስትያን መረጃዎች ማግኘት ይቻላል።

ኢትዮጵያ በሕዝቦቿ የተባበረ ኃይል ወራሪዎችን እየመከተች የቆየች እንጂ በቅኝ ያልተያዘች አገር ከመሆኗም በላይ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅትን ቻርተር ካረቀቁት አገሮች አንዷ ነች። በቅኝ ግዛት የተያዙ የአፍሪካ አገሮችን ነፃ እንዲወጡ እንደነ ኔልሰን ማንዴላ ያሉትን በቅርቡም የናሚቢያን የነፃነት ታጋዮችን በማሠልጠንና ሌሎች በቅኝ አገዛዝ ሥር ለነበሩ አገሮች የቁሳቁስና የዲፕሎማሲ እርዳታ በማድረግ በአፍሪካ የፀረ-ቅኝ አገዛዝ ትግል ከፍተኛ ሚና ተጫውታለች። በ፲፱፻፶፭ ዓም የተመሠረተው የአፍሪካ ኅብረት በኢትዮጵያ መሪዎች የተገኘ ውጤት ነው ። እነዚህ አገራችንና ሕዝቦቻችንን ከሚያኮሩ ብዙዎች ነገሮች ጥቂቶች ብቻ ናቸው።

ኢትዮጵያዊ ሥነምግባር እጅግ የሚየኮራ — ሌብነት፣ ቅጥፈት፣ ሰውን በግፍ መግደል በየትኛውም እምነት የተወገዘ (taboo) ነው፤ እንኳንስ በሰው ላይ በእንሰሳት ላይ አንኳ ግፍ መፈጸም ከጥንት ጀምሮ በኢትዮጵያ ውጉዝ ነው። ዛሬ በአገራችን ከአሥራአምሰት እስከ ሃያ ሚሊዮን ሕዝብ ሥራ የሌለውና በአጠቃላይ 80% የሚሆነው ሕዝባችን ከድህነት መሥመር /poverty line/ በታች የሚኖር እንደሆነ የሚታወቅ ሲሆን አንደችግሩ መጠን ቢሆን ኖሮ በሌሎች አገሮች የሚፈጸሙ ወንጀሎች መናኸሪያ በሆነ ነበር፤ ሆኖም በዚህ የኑሮ ደረጃ ላይ ካለው ሕዝባችን ውስጥ እናቶች መቀነታቸውን እየፈቱ ያላቸውን ሲለግሱ ማየት የተለመደ ሲሆን፣ በየትኛውም አካባቢ ያለ ሕዝባችን ያለውን አካፍሎ የመኖር ባህል አለው። በበለፀጉ አገሮች በመንፈስ ጭንቀት ራስን ማጥፋት የተለመደ ሲሆን፣ የአገራችን ደሀ እንኳ በቅድስናው ስለሚያምን በተስፋ የተሞላ ስለሆነ መሬት ራሷ አፏን ከፍታ ካልዋጠችው በስተቀር እጁን ለሞት አይሰጥም።
ኢትዮጵያዊ ባህል በእድር፣ በእቁብ፣ ደቦና ሌሎች ማኅበራዊ ተቋሞች ተባብሮ ተጋግዞ መኖር ነው። ከመልካም ባህሎቿ መገለጫዎች ውስጥ ጋብቻ የተከበረ ተቋም ነው።

ቅዱስ ጋብቻ፤
ጋብቻ በሌላ አገላለጽ ትዳር ይባላል። ትዳር መተዳደር ከሚለው ቃል የተገኘና ኑሮን መሥርቶ በኃላፊነት ባለቤት ሆኖ ቤተሰብ ማስተዳደር ማለት ነው። ስለሆነም አንድ ሰው ትዳር ይዟል ሲባል በመሸበት አዳሪ ከመሆን ወይም ከነጠላነት/ላጤነት/ ወደሰከነና የተከበረ የኅብረተሰብ ሚና ተሸገጋግሮ ቋሚ/ሙሉ/ መተደዳሪያ ይዞ መኖርን ያመለክታል። በጋብቻ ተሳሥሮ ወልዶ ከብዶ መኖር የተቀደሰ ባህላችን ሲሆን በቤተሰብ አባላት መካከል ያለው መደጋገፍና መተሳሰብ በዓለም ላይ ተወዳዳሪ የሌለው ነው፤ ወላጆችን መጦር ወንድምና እህትን ብቻ ሳይሆን ዘመድ አዝማድን ወይም ረዳት የሌለውን የቤተሰብ አካል አድርጎ በሞግዚትነት ማሳደግ፣ ማስተማር ወይም ትዳር ማስያዝ ኢትዮጵያዊ ወግ ነው። ባል (ወንድ) እና ሚስት (ሴት) ተጋብተው ልጆችን በማፍራት የትውልድ ሐረግ የሚፈጠርበት ዓይነተኛ ሥርዓታችን ቤተሰብ ነው።

ጋብቻ ከባህላችን መገለጫዎች ውስጥ መሠረታዊ ሥርዓት ሲሆን በየብሔረሰቡ ያሉትን ዝርዝር የጋብቻ ሥርዓቶች በስፋት ለመግለጽ ጊዜና እቅም የሚጠይቅ ስለሆነ በዚህ ጽሑፍ ትኩረት ለማድረግ የተሞከረው በጋራ ባህሎቿና የኦርቶዶክስ ተዋህዶ እምነትን በሚከተሉት ወገኖች ያለውን ልማድ (tradition) ነው።

ስለጋብቻ መጽሐፍ ቅዱስ እንዲህ ይላል፤ “ እግዚአብሔርም ሰውን በመልኩ ፈጠረው፤ በእግዚአብሔር መልክ ፈጠረው፤ ወንድና ሴት አድርጎ ፈጠራቸው፤ እግዚአብሔርም ፣ ባረካቸውም፣ እንዲህም አላቸው፤ ብዙ ተባዙ ምድርንም ሙሉአት ግዟትም፤ የባህርን ዓሣዎች የሰማይን ወፎች በምድር ላይ የሚንቀሳቃሱትንም ሁሉ ግዟቸው” (ኦሪት ዘፍጥረት ፩፡ ፳፯-፳፰)። “እግዚአብሄር አምላክም በአዳም ከባድ እንቀልፍን ጣለበት፤ አንቀላፋም፤ ከጎኑም አንዲት አጥንትን ወስዶ ስፍራውን በሥጋ ዘጋው፤ እግዚአብሔር አምላክም ከአዳም የወሰዳትን አጥንት ሴት አድርጎ ሠራት፤ ወደ አዳምም አመጣት። አደምም አለ፤ ይህች አጥንት ከአጥንቴ ናት፤ ሥጋም ከሥጋዬ ናት፤ እርስዋም ከወንድ ተገኝታለችና ሴት ትባል። ስለዚህ ሰው አባቱንና እናቱን ይተዋል፤ በሚስቱም ይጣበቃል፤ ሁለቱም አንድ ሥጋ ይሆናሉ” ኦሪት ዘፍጥረት ፪፡ ፳፩-፳፬። እንዲሁም በማቴዎስ ወንጌል ፲፱፡ ፬-፮፣ ኦሪት ዘፍጥረት ፪፡ ፳፪-፳፬፣ የሐዋርያው ጳውሎስ መልእክት ወደ ኤፌሶን ሰዎች ም ፭ ቁ ፴፩-፴፪ ሁሉ እንደተገለጸው የእግዚአብሔር ቃል “ሰው አባቱንና እናቱን ይተዋል ከሚስቱም ጋር ይተባበራል፤ ሁለቱም አንድ ይሆናሉ” ይላል።
ዝሙትም ፈጽሞ የተከለከለና ኃጢአት ነው። “አመጸኞች የእግዚአብሔርን መንግሥት እንዳይወርሱ አታውቁምን? አትሳቱ ሴሰኞች ቢሆኑ ወይም ጣኦትን የሚያመልኩ ወይም አመንዝሮች ወይም ቀላጮች ወይም ከወንድ ጋር ዝሙት የሚሠሩ ወይም ሌቦች ወይም ገንዘብን የሚመኙ ወይም ሰካሮች ወይም ተሳዳቢዎች ወይም ነጣቂዎች የእግዚአብሔርን መንግሥት አይወርሱም። (፩ኛ ቆሮንጦስ ፮፡ ፲-፲፩) “ሥጋችሁ የክርስቶስ ብልቶች እንደሆነ አታውቅምን? እንግዲህ የክርስቶስን ብልቶች ወስጄ የጋለሞታ ብልቶች ላደርጋቸውን? አይገባም። ወይስ ከጋለሞታ ጋር የሚተባበር አንድ ሥጋ እንዲሆን አታውቁምን? ሁለቱ አንድ ሥጋ ይሆናል ተብሏልና። ከጌታ ጋር የሚተባበር ግን አንድ መንፈስ ነው። ከዝሙትም ሽሹ። ሰው የሚያደርገው ኃጢአት ሁሉ ከሥጋ ውጪ ነው፤ ዝሙትን የሚሠራ ግን በገዛ ሥጋው ላይ ኃጢአትን ይሠራል (፩ኛ ቆሮንጦስ ፮፡ ፲፭-፲፰)። እንዲሁም በማቴዎስ ወንጌል ፲፱፡ ፲፰-፳ ኢየሱስ ክርስቶስ ለሰዎች በሰጠው ሕግ “አትግደል፤ አታመንዝር፣ አትሥረቅ፣ በሐሰት አትመስክር፣ አባትህንና እናትህን አክብር፤ ባልንጃራችህን እንደራስህ ወደድ” ብሏል። ፩ኛ ቆሮንጦስ ፯፡ ፪-፮ ላይ፣ “ስለዝሙት ጠንቅ ለእያንዳንዱ ለራሱ ሚስት ትኑረው፣ ለእያንድንዲቱ ደግሞ ለራስዋ ባል ይኑራት። ባል ለሚስቱ የሚገባትን ያድርግላት፤ እንደዚሁም ደግሞ ሚስቲቱ ለባልዋ። ሚስት በገዛ ሥጋዋ ላይ ሥልጣን የላትም፤ ሥልጣን ለባልዋ ነው እንጂ፤ እንዲሁም ደግሞ ባል በገዛ ሥጋው ላይ ሥልጣን የለውም ሥልጣን ለሚስቱ ነው እንጂ።…እርስበርሳችሁ አትከላከሉ፤ ራሳችሁን ስለ አለመግዛት ሰይጣን እንዳይፈታተናችሁ ደግሞ አብራችሁ ሁኑ” ይላል።
እግዚአብሔር ጋብቻን የመሠረተው ሰው ብቻውን ከሚሆን ይልቅ ከሚስቱ ጋር እንዲረዳዱ፣ በመንሳዊ አንድነት በፍቅር ተባብረው አንዲኖሩና ዘር እንዲተኩ ነው። ስለሆነም ከዚህ ውጭ የሚደረግ ግንኙነት ሁሉ ሕገወጥና ኃጢአት ነው። ኦሪት ዘሌዋውያን ም ፲፰፡ ፳፫-፳፫ ላይ፣ “ከሴትም ጋር እንደምትተኛ ከወንድ ጋር አትተኛ ጸያፍ ነገር ነውና፤ እንዳትረክስበትም…” ይላል። ኦሪት ዘሌዋውያን ፳፡ ፲-፲፮ እንደተገለጸው የሚያመነዝር ወይም ግብረሰዶም የሚፈጽም ወይም ከእንሳሳ ጋር የሚገናኝ በሞት እንዲቀጣ ያዛል።

ልጅ በወላጆቹና ዘመዶች ታፍሮና ተከብሮ የሚኖርበት ኢትዮጵያዊና ማኅበራዊ ትልቅ እሴት ሲወርድ ሲዋረድ የቆየው ቤተሰብ ሲሆን፣ የመንፈሳዊ መሠረቱ ጥንካሬ በክርስትያኑ ሕዝባችን ብቻ ሳይሆን በሌሎች እምነት ተከታዮች ጭምር ጋብቻ በአገራችን ክቡርና የተቀደሰ ሆኖ ቆይቷል።

ቀደም ሲል ልጅህን ለልጄ እየተባለ ቤተሰቦች የልጆችን ጋብቻ ይወስኑ የነበረው ባህል ዛሬ ኋላ-ቀር ሆኖ ቢታይም በወቅቱ በነበረው ሁኔታ ለቤተሰብ መጠናከር ከፍተኛ አስተዋጽዖ ያደረገና ተቀባይነት የነበረው ባህል ነበር። ለአቅመ አዳምና ሔዋን ያልደረሱ ሕፃናት በቤተሰቦቻቸው ውሳኔ ተጫጭተው አንድ ላይ እንዲያድጉ ከተደረገ በኃላ ዕድሜአቸው ደርሶ በአካል መገናኘት ሲጀምሩ ጋብቻው እውን እየሆነ ይሄድ ነበረ። ሁለቱም ሌላ የሚያውቁት ጓደኛና የፆታ ግነኙነት ስለማይኖራቸው ጋብቻውን ከማክበርና ትዳራቸው እንዲሳካ እንደ አንድ አካል ለአንድ ዓላማ በመቆም ጠንካራ ቤተሰብ ከመገንባት በስተቀር ሌላ ምርጫ አልነበራቸውም፤ ሆኖም ይህ የቆየ ልምድ መሥመሩን ስቶ በተለይ ሴቶች ልጆች ሰብአዊ መብታቸው እየተገፈፈ ቅጥ ያጣ የወንድ ጭቆና እየከፋ ስለሄደ በሕግ የቀረ ሲሆን ሴቷም የመምረጥ ዕድል ልትቀዳጅ ችላለች።

ሆኖም ጋብቻን በነፃ ምርጫ የመፈጸሙ መብት የማያወላዳ ሲሆን ነፃነቱም በአግባቡ ትግባራዊ ካልሆነ የራሱ መዘዝ ሳይኖረው አልቀረም። ዛሬ በሃይማኖት ሥርዓት ካልተገዙ በስተቀር ወንዱም ሆነ ሴቷ ብዙ ጋደኞችን ሲፈትሹ ከቆዩ በኋላ ይጋባሉ፤ በራሳቸው ምርጫ መጋባታቸው በጉልህ የሚታይ የመብት መሻሻል ሲሆን ለወጣቶቹ መሳሳብ ቀጥታና ተዘዋዋሪ ምክንያት (ውበት፣ ሀብት፣ ፀባይ፣ ማህበራዊ ሚና፣ ወዘተ) እንደሚኖር የታወቀ ነው። ሆኖም ሲፈላለጉ የተሳሳቡበት/ የተማረኩበት ነገር ሲለወጥ ወይም ወረቱ ሲያልቅ መውደድ ሚዛኑን ያጣና በሰበብ አስባቡ አለመግባባትና የፍቅር መሻከር ይከተላል። ሲተጫጩ ሊማረኩበት የቻሉበት ነገር የፍቅር መነሻ መሆኑ ባይከፋም በመንፈሳዊ ኃይል ካልተጠናከረ መጀመሪያ ያሳሳባቸው ነገር ቢለወጥ፣ መንፈሳዊ እምነትና የቤተሰብ ጫና በበጎ መልኩ መፍትሔ ሊሰጥ የሚችልበት ኃይል ስለማይኖር የጋብቻው ኅልውና አደጋ ላይ ሊወድቅ ይችላል። ቤተሰብም የመበተን ዕድል ሊያጋጥመው ይችላል። እንዲየውም ሠልጥኗል በሚባለው ዓለም ውስጥ የግለሰብ መብት በከፍተኛ ደረጃ ስሚከበርና ይህም ለማኅበራዊ ፍላጎት ሳይሆን ለግለኝነት የሚያመቻች ስለሆነ በቅዱስነቱ ልጆችን ወልዶ በጋራ በአንድ መንፈስ በማሳደግ ፋንታ ጋብቻ እንደማንኛውም ኮንትራት እየታየ ጥቅሞችን እንደመስጠትና መቀበል ያሉ ቁሳዊ ልውውጥ ተራ ባህርይ ውስጥ ስለሚገባ ማኅበራዊ እሴትነቱና ለዛው ጠፍቶ በሕግ ሽፋን ውስጥ ብቻ እርቃኑን ስለሚቀር ፍቅር አልባ ይሆናል፤ ዓላማውን ለመፈጸም ብቃት ከማጣቱም በላይ ሕልውናውም አስተማማኝ አይሆንም።
በሌላ መልኩ ዛሬ በመብት ስም በተለይም ሠለጠኑ በሚባሉት አገሮች እየተከሠተና አልፎ አልፎም በመንግሥት ደረጃም ዕውቅናን ያገኘው እጅግ አሳፋሪ የሆነው የተመሣሣይ ፆታ ጋብቻ /same sex marriage/ ጉዳይ ሲሆን ኅብረተሰባችን ውስጥ ያልገባ ቢሆንም በተለይ በመደበኛ ትምህርት ቤት በሥነፍጥረት /biological science/ ትምህርት የሰዎች የግል ምርጫ መሆኑን እንዲያይ ተደርጎ የሚማረው ወጣት በማኅበራዊ ኑሮ ላይ የሚያስከትለውን አደገኛነት ጠንቅቆ እንዲያውቀው ማድረግ ያስፈልጋል።

ስለተመሣሣይ ፆታ ግንኙነት ወይም ጋብቻ እግዚአብሔር በሰዶምና ገሞራ ሕዝቦች ላይ ቅጣት በመፈጸም ለዓለም ሕዝብ ትምህርት ሰጥቷል። ይህም በኦሪት ዘፍጥርት ም ፲፰ እና ፲፱ ላይ ተገልጿል። ሰዶምና ገሞራ በሚባሉ በዮርዳኖስ ወንዝ ዳርቻ በሚገኙ ሁለት የጥንት ከተሞች ውስጥ እግዚአብሔር ከፈቀደው የተፈጥሮ የፆታ ግንኙነት ውጭ ወንድ ከወንድ እየተገናኘ ኃጢአት ስለበዛ እግዚአብሔር ከተማውን ከነሕዝቡ ሊያጠፋ እንዳሰበ ለአብርሃም ነገረው። አብርሃምም ጥቂት ንጹሐን ሰዎች ቢገኙ እንዲምርለት ለምኖት ፲ እንኳን ንጹሐን ሰዎች ቢገኙ በነዚያ ምክንያት ሁሉንም እንደሚምርለት እግዚአብሔር ቃል ገባለት። በመሸ ጊዜ ሁለት ሰዎች ወደሰዶም ገቡ፤ ሎጥም በሰዶም በር ተቀምጦ ነበር፤ ሎጥም በእንግድነት ተቀብሎ ያሳድራቸው ዘንድ ለመናቸው፤ በቤቱም አስተናገዳቸው፤ ሆኖም የሰዶም ሰዎች ተሰብስበው እንደተለመደው ሁለቱን ሰዎች በግበረሥጋ ሊደፍሯቸው የቤቱን በር ሰብረው ሊገቡ ሎጥን በታገሉት ጊዜ በሰዎች ተመስለው የመጡት ሁለት እንግዶች መላእክት ስለነበሩ ሕገወጦቹን ሰዎች አሳወሯቸው፤ ሎጥንም አሉት፣ ቤተሰብህን ይዘህ ከዚህ ከተማ ውጣ፤ እኛም ይህን ከተማ እናጠፋዋለን አሉት፤ በዘገየ ጊዜም አዝነውለት እጁን ይዘው አወጡት፤ ወደኋላም እንዳያይ ነገሩት፤ ከነቤተሰቡም ከሰዶም ወጥቶ ከመቅሰፍቱ ሲድን ሰዶምና ገሞራ ከነሕዝቡ ተቃጠሉ፤ ሆኖም የሎጥ ሚስት ወደኋላ ስለተመለከተች የጨው ሀውልት ሆና ቀረች። ከዚህ በኋላ ሕገወጥ የፆታ ግንኙነት ግብረሰዶም ተባለ።

ዛሬ ያለው ችግር በአንዳንድ ማህበረሰቦች ዘንድ እንዲህ ያለ የፆታ ሥርዓት እንደ የግለሰብ ነፃነት ወይም የፆታ ግንኙነት ምርጫ መታየቱ ሲሆን ሊሰመርበት የሚገባው ጉዳዩ በግለሰብ ላይ ብቻ ሳይቆም ቤተሰብን፣ ብዙሓን ሕዝቦችን፣ እንዲሁም አገርን የሚበክል ነገር መሆኑ ነው።
The liberal choice for sexual orientation does not stop on an individual. Homogeneous marriage distorts the basic fabric of the social network reflected in a natural family of parent-offspring relationship by obliterating this human relationship and throwing it into the abyss of mere sexualized instinct.

ባሁኑ ጊዜ በአንዳንድ መንግሥታት የተመሣሣይ ፆታ ጋብቻ መፈቀድ በጥንቃቄ ሊታይ የሚገባው ጉዳይ ነው። ሰዎች በዚያ ባሕርይ በመነደፋቸው ምክንያት ኅብረተሰቡ እየተጸየፋቸው ስላገለላቸው ራሳቸውንም እስከማጥፋት የደረሱ ስላሉ በአብዛኛው መንፈስ መድልዎ /discrimination/ ሳይፈጸምባቸው እንደሌሎች ዜጎች በሰላም የመኖር ነፃነት እንዲኖራቸው ተብሎ አገርን ከማስተዳደር አንፃር እየተወሰደ ያለ እርምጃ ነው አንጂ ትክክል ሆኖ አይደለም ። ለምሳሌ ሲጋራ አጫሾች ሰብአዊ መብት ተጠብቆላቸው በተከለለ ቦታ ማጨሳቸው ምርጫቸው ተቀባይነት አለው ማለት አይለም፤ ሲጋራንም የጤንነት ጠንቅ ከመሆን አያስቀረውም። ከሰብአዊነትና ደህንነት አንፃር የግለሰቦችን ነፃነት ለመጠበቅ የሚወሰደው ሕጋዊ አቋም ወይም አስተዳደራዊ እርምጃ የግለሰቦቹን ጥፋትና ስህተት ትክክለኛ አያደርገውም፣ መቻቻልን /tolerance/ እንጂ። በመንፈሳዊ መንገድም ብናየው እግዚአብሔር ሕግን የሰጠን በፈቃዳችን አንድንፈጽም ሲሆን ሕጉን ባለመከተል ኃጢአት ብንሠራ የምናጣውን ሁሉ ገልጾልናል (፩ኛ ጴጥሮስ ፪፡ ፲፮፣ ገላትያ ፭፡ ፩ የዮሐንስ ወንጌል ፰፡ ፴፩-፴፮)፤ ለመዳን ፈቃደኞች ካልሆንን እና የመዳኛውን ሕግ ትተን የመሞቻውን ነፃነት የምንመርጥ ከሆነ እንጎዳበታለን። ስለሆነም የእግዚአብሔርን ሕግ ከመከተል በስተቅር ሌላ የሚጠቅም አማራጭ እንደሌለ ማውቅ ብልህነት ነው።

የተፈጥሮ ቤተሰብና ሚናው፣
ሰው ሊወለድ የሚችለው ከተፈጥሮ እናትና አባት ብቻ ነው። ሆኖም በማደጎ እጅ ላይ የወደቀ ልጅ የማደጎ ወላጆቹ ምንም ያህል ደጋግ ቢሆኑ የማንነት ጥያቄ ማንሳቱ አይቀርም፤ ይህ ደግሞ የሥነልቡና ችግር ይኖረዋል። ወላጆቻቸው የሞቱባቸው ልጆች እንኳ ከማደጎ ወላጆች ጋር የሚኖራቸው ግንኙነት እስከሞት ድረስ ያደረሰ ቀውስ ማስከተሉ በየጊዜው በዜና ማሠራጫዎች ይሰማል። በአሜሪካን አገር ብቻ ከ፲፱፻፹፱ እስከ ፳፻፲፫ ዓም በማደጎ ከውጭ አገር ከመጡ ሕፃናት ውስጥ ፪፻፺፫ ሞትና ሌላ ከባድ ጉዳት እንደደረሰባቸው ኒጌል ባርበር የተባለ ሳይኮሎጅስት ካቀረበው ስታትስቲከስ ታውቋል።

የተመሣሣይ ፆታ ጋብቻ ብለው ግብረሰዶማውያን የሚጠሩት እውነተኛ ጋብቻ ሳይሆን ሕገወጥ እና በወሲብ ላይ ያተኮረ ግንኙነትና ዝሙት ነው። በአሁኑ ጊዜ ዓለምን እየበከለ ያለው የተመሣሣይ ፆታ ጋብቻ ዓላማው ፍትወተሥጋ (ወሲብ) ብቻ ሲሆን ብዙ ተባዙ ምድርንም ሙሉአት የሚለውን አምላካዊ ቃል የሚፃረር ስለሆነ ልጆች ከወላጆቻቸው ውጭ በእንጀራ እናት ወይም እንጀራ አባት ሥር ስለሚያድጉ የእናት-አባት የወንድም-እህት ወዘተ ቤተሰባዊ ፍቅርና ጣእም ከቶውንም ያጣሉ። ምክንያቱም ከተቃራኒ ፆታዎች (ባልና ሚስት) ውጭ የሚጋቡ ሰዎች ልጅ ለማግኘት በማደጎ ማምጣት አለበለዚያም አመንዝራ የመፈጸም ምርጫ ውስጥ ይገባሉ። እግዚአብሔር ለሰዎች የፈቀደውን የወላጅ-ተወላጅ የተፈጥሮ ሕግ ተከትሎ በቤተሰባዊ ግንኙነት ማኅበራዊ ኑሮ በመኖር ፋንታ እንደ እንሰሳ በዘፈቀደ የመገናኘትና አንደከብት የአባቱን ማንነት ጥያቄ ውስጥ የሚጥል ተወላጅን (offspring) ያስከትላል። በዚህ መልክ ልጆች የተባሉ ተወላጆች ሁሉ እውነተኛ አባትና እናት ሳይሆን በማደጎ ወላጆች ሥር ስለሚያድጉ ይህ የትውልድ ሐረግን ስለሚያጠፋ ሰዎችን በዝምድና ማየት ሳይሆን በአካል ብቻ የመቁጠር ዕድል ስለሚያስከትል ፍቅር፣ ኃላፊነት፣ ሞራል፣ የማንነት ጉዳይ…ወዘተ እየደበዘዙ ሰብአዊነት በእንሰሳዊ ባሕርይ ይዋጣል።

ቤተሰብ ከእግዚአብሔር የተሰጠን በረከትና ልጆች በማኅበራዊ ፍጡርነት ከእግዚአብሔር በተሰጣቸው ፀጋ ፍቅርን የሚያዩበት፣ የሚገልጹበት ትንሹ የኅብረተሰብ ሕዋስ ነው። “ዞሮ ዞሮ ከቤት ኖሮ ኖሮ ከመሬት…” እንደሚባለው ቤተሰብ ተወዳዳሪ በሌለው መስዋዕትነት የተፈጥሮ ፍቅር የሚተገበርበትና ልጅ በወላጁ፣ ወላጅ በልጁ..ወዘተ ፍጹም ተስፋ የሚጥልበትና የሚመካበት የአለኝታነት መገለጫ ነው፤ ቤተሰብ የሰዎች ሰብአዊ ክብርና የትውልድ ሐረግን ተከትሎ የሚመጣ ወግና የማንነት መግለጫ ነው፤ ቤተሰብ በተፈጥሮ የሚተማመኑበት የአንድነትና የባለቤትነት መገለጫ አካል ነው፤ ቤተሰብ የራሴ ከሚሉት አካል ጋር በእውነት ስለ እውነት ከምንም ጋር በማይተካከል ነፃነት የሚገናኙበት በእግዚአብሔር ፀጋ የተገኘ ሕዋስና ርህራሄን፣ ምህረትን፣ ይቅርታንና ልግሰናን የሚያገኙበት ትንሹ መንግሥት ነው፤ ቤተሰብ ተወዳዳሪ በሌለው ቅንነት ኃላፊነት የሚፈጸምበት የኅብረተሰብ አካል ነው። ቤተሰብ ይህን ሁሉ ማኅበራዊ እሴት ተሸክሞ የሚቆም የኅብረተሰብ ምሰሶ ነው። ነገር ግን ከላይ እንደተገለጸው የተመሣሣይ ፆታ ግንኙነት ሕገወጥ ከመሆኑም በላይ ቤተሰብን መሠረት ያሳጣዋል።

መልካም ባህላችንን ጠብቀን ለሌላው ዓለም ማስተማር፣
ምሰሶ ከተዛባ ቤት እንደሚናጋ ሁሉ ቤተሰብም ከእግዚአብሔር የተሰጡትን ማኅበራዊ እሴቶች መሠረት ካጣ ኅብረተሰብ ይናጋል፤ የሰው ልጅም መንፈሳዊ ኃይሉን ስለሚያጣና ለእንሰሳዊ /instinct/ ሥጋዊ ፍላጎት በመገዛት ሙሉ ሰብአዊነቱን ስለሚያጣ የራሱን ክብር ዝቅ ያደርጋል። በዚህ የተነሣ መንፈሳዊ ሙሉነት አይሰማውም። ሰብአዊ ክብሩን የማይጠብቅ ሰው ጥሩ ማኀበራዊ ባህል ሊኖረው አይችልም። ፍቅር፣ ኃላፊነት፣ ይሉኝታ፣ ሞራል በተሞላበት ማኅበራዊ ባህል ያልተገነባ ቤተሰብ ደግሞ ለቁሳቁስና ግብረሥጋ ግንኙነት የሚተባበር ልቅ የሰዎች ስብስብ ስለሚሆን ለማናቸውም ሕገወጥ ተግባሮች የተጋለጠ ነው፤ ምክንያቱም ሥጋዊ ፍላጎቱን ሊገዛ ካልቻለ እንኳንስ ለመንፈሳዊ ሕይወት ቀርቶ ሰው-ሠራሽ ለሆነውም የመንግሥት ሕግ መገዛት አይችልም። ስለዚህም ነው የአመንዝራ ትውልድ እየበዛ የአንድ ወላጅ ልጆች የሚበዙበትና ስብእናቸው ያልተሟላ ስለሚሆን ቁሳዊ ችግር እንኳ ሳያግጥማቸው ሰዎች በመንፈስ ጭንቀት ሐሳርና መቅስፍት የሚደርስባቸው።

ሰው ራሱን መግዛት አቅቶት በሥጋዊ ፍላጎቱ ከተሸነፈ ለእንስሳዊ ባህርይ ስለሚገዛ የራሱን ሰብአዊ ክብር ከማጣቱም በላይ የቤተሰቡን /ዘመዶቹን/ የተፈጥሮ ግንኙነት በጣጥሶ ህልውናቸውን ያጠፋል። ቤተሰብ ጠንካራ ማኅበራዊ መሠረት ከሌለው ደግሞ አንድነት የሌለው በደመነፍስ ፍላጎት የተሞላ የግለሰቦች ጥርቅም ስለሚሆን አጥንት እንደሌለው ሥጋ የመፈራረስ ዕድል ውስጥ ይወድቃል። የቤተሰብ መዳከም ደግሞ የኅብረተሰብን ድርና ማግ ይበጣጥሰዋል፤ ይህም መልካም ሰብእናን የሚያሳሳ ስለሚሆን የአገርን ማኅበራዊ እሴቶች በማጥፋት ዜጎችን ከኅብረተሰቡ ጋር ትሥሥር ሳይኖራቸው የግል ፍላጎታቸውንና ጥቅማቸውን ለማሟላት ብቻ የሚፈልጉ በዘፈቀደ ስሜት የሚመሩ የግለሰቦች ክምችት በማድረግ ሰብአዊነትን ስለሚያጠፋ ለመልካም አስተዳደር መጓደል ከፍተኛ አስተዋፅዖ ሊያደርግ ይችላል።
“እንሰሳ ሰው ሆነ ሰውም እንሰሳ ሆነ” እንደተባለው ከኅብረተሰባችን ውጭ ያሉትም ቢሆኑ በአርዓያሥላሴ የተፈጠሩ ስለሆኑ በዚህ መነሻውም ሆነ መድረሻው ወሲብ ብቻ በሆነ ባህርይ እየተለከፉ ከሄዱ ይህ ልምድ ለሥጋቸውም ሆነ ለነፍሳቸው የዘለቄታ ጥቅም ስለሌለውና በመጨረሻም ትውልዳቸውን ጭምር እያበላሸ ተጨማሪ ማህበረሰቦችንም ሊበክል ስለሚችል ከዚህ ልምድ እግዚአብሔር እንዲያወጣቸው ልንፀልይላቸው ይገባል። ሆኖም በእነዚህ ርካሽ በሆኑና በእንሰሳዊ ደመ-ነፍስ (instinct) ባህርይ በተበረዙ ልማዶች የራሳችንን መልካም ባህል ማዳከም የለብንም፤ የአገራችንን የጋብቻ ሥርዓት በአጠቃላይም በመልካም ባህላችን ውስጥ ያሉ ማኅበራዊ እሴቶቻችንን እያዳበርን ልንጠብቃቸው እና ሌሎችን ኅብረተሰቦች ልናስተምራቸው ይገባናል እንጂ።
ይህ ክስተት ወደ ባህላችን ዘልቆ ስላልገባ አሳሳቢ የማይመስላቸው የዋህ ወገኖች አሉ። ይኽም ራሷን አሸዋ ውስጥ ደብቃ የሚሆነውን ሁሉ አላይም ብላ የቀረውን አካሏን ለአደጋ እንደተወችው እንሰሳ እንደመሆን ነው። ሆኖም ዛሬ ዓለም እየተቀራረበች ባለችበት ዘመን በተለይ ወጣቱን ትውልድ በቅድሚያ በማስተማር በአገሩ ባህል ሙሉ እምነት አድሮበት ከዚህ መጥፎ ባህል ራሱን እንዲጠብቅ በወቅቱ ማስገንዘብ ይመረጣል።

አዲስ ፕሬዚደንት በአዲስ ዓመት –በተክሉ አባተ

0
0

ይድረስ ለአቶ አንዳርጋቸው ፅጌ ፡

unknown_personጤና ይስጥልን አቶ አንዳርጋቸው እንደምን አሉ ፤ በኢሳት መስኮት እንዳየሁዎ ጤናዎ በመልካም ሁኔታ ላይ ይገኛል ብየ እገምታለሁ ። እንደባህላችን ከብቶቹስ እንዴት ናቸው እንዳልልዎ ኤርትራ ከብት ለማርባት እንዳልሄዱ አውቃለሁና ምንም እንዲሉኝ አልጠብቅም ። ልጆቹስ እንዳልል መንታዎቹ ልጆችዎ በ single  mother ለንደን በእንክብካቤ እያደጉ መሆኑን ስለሰማሁ በጥያቄ አላስቸግርዎትም ። ትግሉ ብል ይሻላል እንዴት ነው እየሰመረ ነው ? በረሃውን እየለመዱት ነው ? በቃ የግንቦት ሰባት ህዝባዊ ህይል በየጦር ሜዳው ወያኔን እያርበደበደው ነው አይደል ? እንግዲህ አራት አመት ሞላዎ እኮ ! ዘመኑ እንዴት ይሮጣል ጃል ።  ቀጣዩን ለማንበብ እዚህ ይጫኑ

ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ፣ የአንድነት ለዴሞክራሲ እና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) ሊቀ መንበር አንዱአለም አራጌ የአመቱ ሰው ተብሎ በመሰየሙ የተሰማቸውን ደስታ ገለጹ

0
0

ትርጉም  በግርማ ሞገስ

 

ዶር ነጋሶ ጊዳዳ፣ የአንድነት ለዴሞክራሲ እና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) ሊቀ መንበር አንዱአለም አራጌ የአመቱ ሰው ተብሎ በመሰየሙ የተሰማቸው ደስታ ለመግለጽ በእንግሊዘኛ የፃፉት መልዕክት በጥያቂያቸው መሰረት ከሞላ ጎደል እንደሚከተለው ቀርቧል።

 

ቅዳሜ መስከረም 4 ቀን 2006 ዓ.ም. 
Saturday, September 14, 2013

 

አንዱአለም አራጌና ቤተሰቦቹ

አንዱአለም አራጌና ቤተሰቦቹ

“ዘሐበሻን እና ሌሎች ሚዲያዎችን የመድረስ አቅም ያላቸው እህቶቻችን እና ወንድሞቻችን አንዷለም አራጌን የአመቱ ሰው አድርገው መምረጣቸውን መስማቴ ታላቅ ደስታ ሰጥቶኛል። አንዷለም ለህዝቡ እና ለአገሩ ብዙ ያበረከተ እና የተጠየቀውን መስዋዕት ሁሉ ካለ ምንም ስስት የከፈለ እና በመክፈል ላይ የሚገኝ ድንቅ ግለሰብ በመሆኑ ለአንዷለም ይኽን እውቅና በመለገሳችሁ ላመሰግናችሁ እወዳለሁ።

እንደ ኢትዮጵያ አቆጣጠር በ1998 ዓ.ም. ከእስር ቤት ከወጣበት ጊዜ ጀምሮ በተለይ ደግሞ መድረክን ወደ ህብረት ከፍ ለማድረግ የፖለቲካ ፕሮግራም እና መተዳደሪያ ደንብ አብረን መቅረጽ ከጀመርንበት ጊዜ ጀምሮ አንዷለምን አውቀዋለሁ። ብዙ ፍሪያማ አሳቦችን ለግሷል። መድረክ ወደ ግንባር ደረጃ እንዲደርስ ለማድረግም ካለምንም መታከት ሰርቷል። አንዷለም አንድነት ፓርቲን ወክሎ በመድረክ ስራ አስኪያጅ ኮሚቴ ወስጥ በነበረበት ጊዜ ለመድረክ ፕሮጀክት መሳካት ብዙ ከጣሩት የአንድነት ሰዎች ውስጥ አንዱ ነበር። ለወቅቱ የመድረክ ሊቀመንበር ፕሮፌሰር በየነ ጴጥሮስ አክብሮት ነበረው። እጅግ ቀና የሆነ የስራ ግንኙነት ነበራቸው። ያኔ እንደማውቀው እና ዛሬም እንደሚመስለኝ አንዷለም መድረክን በሚመለከት ከአንድነት ከሚሰሙ አሉታዊ ድምጾች ጋር አይስማማም። ቀደም ሲልም በዚህ ጉዳይ ላይ ጽኑ ክርክሮች አድርጓል።

 

አንዷለም ከመኢአድ እና ያኔ ከአንድነት ተነጥለው ከሄዱት ወገኖች (ዛሬ ሰማያዊ ፓርቲ) ጋር ውህደት እንዲደረግ ይፈልግ ነበር። በዚህ አቅጣጫ አንዷለም የአንድነት ፓርቲን ስራ አስኪያጅ ኮሚቴ አግባብቶ ወይዘሮ ላቀች ደገፉ እና አቶ ተመስጌን ዘውዴ ያሉበትን የድርድር ኮሚቴ ፓርቲው እንዲመሰርት አድርጎ ነበር። ሁለተኛ እስር እስከተበየነበት ጊዜ ድረስ ለዚህ ጉዳይ መሳካት በመስራት ላይ ነበር አንዷለም።

 

አንዷለም ቁርጠኛ የሰላማዊ ትግል ተዋጊ ነበር። የማህተማ ጋንዲ እና የማርቲን ሉተር ተከታይ። የፖለቲካ እንቅስቃሴዎቹ የሚመሩት በእነዚህ ሁለተ ሰዎች ትምህርቶች ነበር። አንዷለምን ሽብርተኛ ነው ወይንም ከሽብርተኞች ጋር ግንኙነት ነበረው ብለው የሚያስቡ ሰዎች ካሉ አዕምሮዋቸውን የሳቱ እና እራሳቸው ሽብርተኞች ናቸው።

 

አንዷለም የአንድነት ጸሐፊ እና የአንድነት ህዝብ ግንኙነት ኮሚቴ ሊቀመንበር በነበረበት ጊዜ ለድርጅቱ ስኬት ለሊት እና ቀን ሰርቷል።

ባለቤቱን እና ሁለት ልጆቹን ይወድ ነበር። ቀኑን እና ምሽቱን ለአንድነት ሲሰራ ውሎ ምሽት ላይ ወደ ቤተሰቡ ነበር የሚሄደው። ወደ መዝናኛ ቦታዎች ከመሄድ ፈንታ።

 

ዶር ነጋሶ ጊዳዳ፣ የአንድነት ለዴሞክራሲ እና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) ሊቀ መንበር

ዶር ነጋሶ ጊዳዳ፣ የአንድነት ለዴሞክራሲ እና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) ሊቀ መንበር

የግል ህይወቱን በሚመለከት፣ አንዷለም የመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርቶችን በንጹሕ ልቦና የሚከተል መንፈሳዊ ሰው ነው። አንዷለም “ ግራ ፊትህን በጥፊ ለመታህ ሰው ቀኝ ፊትህን ስጠው። ሌሎች በአንተ ላይ እንዲፈጽሙብህ ያማትፈልገውን አንተም በሌሎች ላይ አትፈጽም።” የሚሉት የእየሱስ ክርስቶስ ትምህርቶች ተከታይ ሰው ነው። ሰው አስቀይሞ ወይንም ተሳድቦ አያውቅም። ሲሰደብም መልሶ አይሳደብም። አይበቀለም አንዷለም። ምክርን እና ማጽናናትን ለሚሹ ሁሉ አንዷለም ጊዜ ነበረው።

 

አንዷለም አዕምሮ-ክፍት እና ግልጽ ሰው ነው። የማዳመጥ ልዩ ችሎታ አለው።

 

አንዷለምን “የአመቱ ሰው” ብላችሁ መምረጣችሁ ትክክለኛ ውሳኔ ነው። ይገባዋል። ለሁላችሁም ምስጋናዬ ይድረሳችሁ።

 

ዶር ነጋሶ ጊዳዳ፣

 

የአንድነት ሊቀመንበር”

 

 

 

የፖለቲካ ኃይል ምንጮች ክፍል አንድ/2፡ የዝንጀሮዎቹ ጌታ ሞተ –ለምን እና እንዴት? ከግርማ ሞገስ

0
0

ግርማ ሞገስ (girmamoges1@gmail.com)
ሰኞ መስከረም 6 ቀን 2006 ዓ.ም. (September 16, 2013)

Girma Moges

አቶ ግርማ ሞገስ

የዝንጀሮዎቹ ጌታ አጭር ታሪክ የተወሰደው ቻይናዊው ሊዩ ጂ/ Liu-Ji (1311-1375) ከጻፈው የሞራል ማስተማሪያ መጽሐፍ ነው። ይኽ አጭር ታሪክ የአምባገነን ገዢዎች የፖለቲካ ኃይል ከየት እንደሚፈስላቸው (ምንጩ ምን እንደሆነ) እና እንዴት ምንጩን በመቆጣጠር የአምባገነኖችን አቅም መቆጣጠር አልፎም ምንጩን በማድረቅ አምባገነኖችን ማስራብ እንደሚቻል በምሳሌ አድርጎ ግልጽ ያደርጋል። ሰለዚኽ የሰላማዊ ትግል ተመራማሪው እና ዘመናዊ የፖለቲካ ሳይንስ ጠበብቱ ሲድኒ ታይ (Sidney Tai) ከቻይንኛ ወደ እንግሊዘኛ ቋንቋ ተረጎመው። የእንግሊዘኛ ትርጉሙን “በማጭበርበር መግዛት” (“Rule by Tricks”) የሚል ርዕስ ሰጠው እና ሰላማዊ ቅጣቶች (Nonviolent Sanctions) በሚል ርዕስ የአልበርት አነስታይን ሰላማዊ ትግል ምርምር ተቋም በሚያትማት ጋዜጣ ላይ አሳተመው ሲድኒ ታይ (Sidney Tai)። የዝንጀሮዎቹ ቅጣት ሰላማዊ ቅጣት እንደነበር እና የዝንጀሮዎቹ ጌታ ቅጣት ግን የኃይል ቅጣት (Violent Sanction) እንደነበር ወደፊት ከቦታው ስንደርስ እናስተውላለን። በቅርብ ደግሞ ጂን ሻርፕ (Gene Sharp) የተባለው ሌላው የዘመናችን የሰላማዊ ትግል ተመራማሪ እና በካምብሪጅ ዩንቨርስቲ መምህር ይኽን አጭር ታሪክ ከአምባገነን ወደ ዲሞክራሲ በሚለው መጽሐፉ ገጽ 17-18 ላይ ሰላማዊ ትብብር የመንፈግ ትግል (Nonviolent Non-cooperation Struggle) የሚለውን የሰላማዊ ትግል ጽንሰ አሳብ ለማብራራት ተጠቅሞበታል። የዚህ ጽሑፍ ግብ በዚህ አጭር ታሪክ አንባቢዎች እየተዝናኑ እንዲመራመሩ ማድረግ ነው። ይኽ ምርምር በቅርብ ለንባብ ለማቀርበው ጽሑፍ መሰረት ይጥላል የሚል እምነት አለኝ።   ቀጣዩን ለማንበብ እዚህ ይጫኑ  

 

የምስራች ለኢህአዴግ የምጡቅ ጭንቅላት ባለቤትነት ምልክቶች በአንድ ካድሬ ተገኘ

0
0

ከዳዊት ሰለሞን (ጋዜጠኛ)

ኢህአዴግ መለስን በተፈጥሮ ሞት እንደተነጠቀ የድርጅቱ አመራሮች የሙሉ ጊዜ አገልግሎቱን ለለቅሶው ባበረከተው ቴሌቪዥን በመቅረብ ሟቹ መለስ የምጡቅ ጭንቅላት ባለቤት እንደነበሩ ይናገሩ ነበር፡፡የኢህአዴግን አቅጣጫ የሚቀይሱ፣የትግራይን ስትራቴጂክ እቅድ የሚነድፉ፣የድርጅቱን የንድፈ ሃሳብ መጽሄት በዋና አዘጋጅነት የሚያገለግሉ፣የአገሪቱን የጦር ሃይል በ1997 ጠቅልለው ወደ ራሳቸው ዕዝ ያስገቡ፣ዶክተሩን፣መምህሩን፣ተማሪውን፣አርቲስቱን፣ወጣቱን፣በንግራቸው የሚያማልሉ፣የአፍሪካ አዲስ ተስፋ ተሰኝተው በእነ ቶኒ ብሌር የተመረጡ፣የአገር ውስጡን ተቃዋሚ ጣት እቆርጣለሁ በማለት የሚያስፈራሩ፣እነዚህና ሌሎች ስንክሳሮች ተመዝዘው መለስ‹‹የምጡቅ ጭንቅላት ባለቤት ናቸው ››ተባሉ፡፡ከመለስ በኋላ ይህን ጭንቅላት ስለ ማግኘቱ የተነገረለት ወይም አለኝ ያለ እስከ ዛሬ ማለዳ አላጋጠመኝም ነበር፡፡
በመለስ እግር የገቡት አቶ ሃይለማርያም ደሳለኝ የመለስ ጫማ እንዳልበቃቸው በመታመኑ በክላስተሮች የተከፋፈሉ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሮች ተመደቡላቸው ወይም ተመደቡባቸው፡፡(ሂደቱን አንዳንዶች በጠቅላይ ሚኒስትሮች ብዛት አገራችን እመርታ አስመዘገበች በማለት መቀለዳቸውን አስታውሳለሁ)ነገር ግን ለእኔ ሹመቱ የእመርታ ጉዳይ ሳይሆን ያን ምጡቅ ጭንቅላት በአንድ ሰው መተካት አለመቻሉን ኢህአዴግ ማመኗን የሚያሳብቅ ነው፡፡

(የፎቶ ምንጭ አዲስ ፎርቹን ጋዜጣ)

(የፎቶ ምንጭ አዲስ ፎርቹን ጋዜጣ)


ኢህአዴግ አንዱን መለስ በብዙ ለመተካት እየወሰደ ከሚገኘው እርምጃ በተቃርኖ ዳንኤል ብርሃነ የሚባል ግለሰብ የምጡቅ ጭንቅላት ባለቤት ነኝ››በማለት ራሱን አስተዋውቋል፡፡ይህ ምጡቅ ጭንቅላት በመፈለግ ከመለስ ሞት በኋላ በቀን ብርሃን ባትሪ እያበራ ሲፈልግ ለከረመው ኢህአዴግ ትልቅ የምስራች ነው፡፡
ወዳጄ እርስዎ ‹‹ምጡቅ ጭንቅላት››የሚል ቃል ሲያደምጡ ወደ አይነ ህሊናዎ የሚመጡት እነ አልበርት አነስታይን፣ሊዮ ቶሎስቶይ፣አጼ ምኒልክ፣ማዘር ቴሬዛ፣ኔልሰን ማንዴላና ሌሎች ይሆናሉ ፡፡በኢህአዴግ ማውጫ የምጡቅ ጭንቅላት ባለቤትነት ሁሉን በጠላትነት አይን ማየት፣ዘረኝነት፣ፍረጃ፣አማራጭ የሚባል ሃሳብ ጠረጴዛው ላይ እንዳይቀርብ የተለየ ሃሳብ አመንጪን መምታት ነው፡፡በዚህ ረገድ የፌስ ቡኩ ዳንኤል ብርሃነ ‹‹የምጡቅ ጭንቅላት ባለቤት ስለ መሆኑ መከራከር ጉንጭን ማልፋት ነው፡፡የህግ ባለ ሞያና የምጡቅ ጭንቅላት ባለቤት ነኝ የሚለን ግለሰቡ በቅርቡ ፖስት ያደረጋቸውን ወይም አስተያየት የሰጠባቸውን አንዳንድ ጹሁፎች በመመልከት ምጡቅ ጭንቅላት እኛ በምናውቀውና እነርሱ በሚሉት መካከል የሰማይና የምድር ያህል ልዮነት እንዳለው እንገነዘባለን፡፡
Wossi Zebdewos:- ”There was a defection news/ Rumor at the first place??”

Daniel Berhane:- ”Yes, there is such a news from the enemies of Tigrai.”
ዘብዴዎስ የተሰኙ የፌስ ቡክ ተጠቃሚ ለዳንኤል እነ አርከበን በተመለከተ የኩብለላ የጭምጭምታ ዜና ከመነሻው ስለ መኖሩ ይጠይቁታል፡፡ዳኒ በመልሱ ‹‹አዎን ከትግራይ ጠላቶች እንዲህ አይነት ወሬ ነበር››ብሎ ቁጭ፡፡በቃ በእርሱ ምጡቅ ጭንቅላት ውስጥ እነ አርከበ ኮበለሉ ማለት የትግራይ ጠላት መሆን ነው፡፡ የባለስልጣኑን ኩብለላ ከትግራይ ጠላትነት ጋር ሊያቆራኝ የሚችል የዳንኤል ምጡቅ ጭንቅላት ካልሆነ በቀር እንዲህ አይነት ጭንቅላት ማግኘት ያስቸግራል፡፡እንቀጥል
Daniel Berhane:- #Ethiopia: History repeats itself. Now Arena-Tigray is the enemy with-in.
አረና በቀድሞ የህወሃት ከፍተኛ አመራሮች የተመሰረተ ፓርቲ ነው፡፡ዳንኤል ይህንን ፓርቲ እንዴት እንደሚመለከተው ሲጠቅስ በውስጥ ያለ ጠላት ብሎታል፡፡በቃ ለዚህ ምጡቅ ጭንቅላት ህወሃትን መቃወም ጠላትነት ነው፡፡አረና በትግራይ ምድር ሆኖ ህወሃትን መቃወሙን ደግሞ በውስጥ ያለ ጠላት በማለት እንዲፈርጅ አድርጎታል፡፡ምን ይደረግ የምጡቅ ጭንቅላት ባለቤት ነዋ፡፡አሁንም ከዳንኤል ይቅርታ ከምጡቅ ጭንቅላት ጋር ነን፡፡
Daniel Berhane:- በትግራዮች እና በኢሕአዴግ አባላት ላይ ማህበራዊ መገለልን ያወጃቹሁ ሰዎች(ጨዋው የኢትዮጲያ ሕዝብ አሳፈራችሁ እንጂ)፣ በተግባርም የትግራዮች ቤት ሲቃጠል እና ‹‹የሚቃጠል›› ተብሎ ሲፃፍበት ግድ ያልሰጣችሁ ሰዎች፣ የበድሩ አደምን ዘረኛ መፈክር ከማውገዝ ይልቅ የቃላት ጨዋታ የመረጣችሁ ሰዎች፣ በእናንተ አመራርና ቅስቀሳ ስለተደበደቡና ስለተገደሉ ትግራዮች ከመቆጨት ይልቅ መከራከር የመረጣችሁ ሰዎች፣ እንኳን በፈቃዳችሁ መራብ ቀርቶ ምግብ አጥታችሁ ብትራቡ ግድ የሚሰጠው የሚኖር ይመስላችላኋል
ደረጄ ሀብተወልድ የጋዜጠኛ ርዕዮት አለሙን የርሃብ አድማ በማስመልከት የዳንኤል ወንድሞች የሰጡት ምላሽ አበሳጭቶት እነርሱ እኮ ለቅንጅት አመራሮች የርሃብ አድማ የሰጡት መልስ ተመሳሳይ ነበር እናም ርዕዮት የርሃብ አድማ በመጀመሯ ያዝናሉ ብለን መጠበቅ አይገባም፡፡ይላል ዳኒ ለደረጀ መልስ በመጻፍ‹‹እንኳን በፈቃዳችሁ መራብ ቀርቶ ምግብ አጥታችሁ ብትራቡ ግድ የሚሰጠው የሚኖር ይመስላችላኋል››ምጡቅነቱን አሳየን፡፡አዎን በዳንኤል ዙሪያ ግድ የሚለው ላይኖር ይችላል፡፡እናንተ ግድ እንዲላችሁ ነፍስ መበላለጥ አለበት፡፡ደግሞስ ይህን ዘረኛ ከፋፋይ የፖለቲካ እሳት እንዲዛመት ያደረጋችሁት እናንተው መሆናችሁን መዘንጋት አይኖርብህም፡፡በጣም ግራ ያጋባኝ ነገር ድሬዳዋ ያደገ ሰው በድሬ የተማረ ከየት ነው ይህንን ዘረኛ አመለካከት የያዘው?
Daniel Berhane:- It is boring to see such a long collection of stupid comments. If you don’t like the info, go hang yourselves.
ዳንኤል ለለጠፈው ጽሁፍ በዛ ያሉ ሰዎች ተቃራኒ አስተያየት መሰንዘር በመጀመራቸው ባለ ምጡቅ ጭንቅላቱ ‹‹እኔ የሰጠሁት መረጃ ያልተመቸው ራሱን ማጥፋት ይችላል ብሎ አረፈው፡፡ጠላትነት፣ራስን ማጥፋት፣ማንም ስለ እናንተ ግድ የለውም፣የትግራይ ጠላቶች ››የሚሉ ቃላትን በዳኒ እያንዳንዱ ጽሁፍ ውስጥ ተሰግስገው ያገኛሉ፡፡እነዚህን ቃላትም መለስ በህይወት ዘመናቸው የተካኑባቸው እንደነበሩ ካስታወሱ ቃላቶቹ ምጡቅ በመሆን የሚገኙ ወይም የምጡቅነት መለኪያ መሆናቸውን ይረዳሉ፡፡

Daniel Berhane:- ርዐዮት ሐኪም ተከለከለች በለኝ – ምንም ማድረግ ባልችል አብሬ እታመማለሁ፡፡
ፍቅረኛዋን በዚህ ቅዳሜና/እሁድ ሳታገኝ ቀረች በለች አዝናለሁ፡፡
ሌላው የሚዲያ ሰርከስ አይመለከተኝም፡፡
ወዳጄ ስላቁን ተመልከቱ፡፡የርእዮትን የርሃብ አድማ ፍቅረኛዋን ከማግኘት ጋር በማቆራኘት እቃቃ ሊያደርገው ይሞክራል፡፡አስረኛዋ በማንም የመጎብኘት ፍቅረኛዋን ጨምሮ መብት አላት፣ህክምና ማግኘትም የታሳሪ መብት ነው፡፡ወደ ጡት ካንሰርነት ሊያደግ የሚችል እጢ እንዳለባት የተነገራት ሴት የህመሙን እድገት ለመቀነስ የተመረጠ ምግብ መብላት፣ጭንቀት ከሚፈጥር ሁኔታ መራቅ ይገባታል፡፡የጀመረችው የርሃብ አድማ ደግሞ በተቃራኒው ለህመሙ መፋጠን የራሱን አስተዋእጾ ያበረክታል፡፡ምጡቅ ሆይ ሰብዓዊነት ግድ ሊለን አይገባም ይሉን ይሆን?አብረው የሚታመሙ ከሆነ ምነው አብረዋት ባይራቡ የመራቧን መንስኤ ባያወላግዱት?ረስቼው ምጡቅነት ለካ ለሰብዓዊነት ቦታ የለውም፡፡

ቀነኒሳ በቀለ ሞ ፋራህን በግማሽ ማራቶን ቀጣው፤ መሠረት እና ጥሩነሽ 2ኛና 3ኛ ወጡ

0
0

kenenisa 1(ዘ-ሐበሻ) ዛሬ በሰሜን እንግሊዝ ታላቁ የግማሽ ማራቶን ሩጫ ውድድር ኢትዮጵያውያን አትሌቶች የተሳካ ውጤት አስመዘገቡ። ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ለኢትዮጵያዊያን አትሌቶች ራስ ምታት ሆኖ የነበረውና በ5 ሺህ እና በ10 ሺህ ሜትር የወርቅ ሜዳሊያዎችን ሲጠቀልል የነበረው እንግሊዛዊው አትሌት ሞ ፋራህ ዛሬ በሃገሩ ላይ በቀነኒሳ በቀለ ተቀጥቷል።

ቀነኒሳ በቀለ በዛሬው ውድድር ሞ ፋራህን ያሸነፈው ውድድሩን በአንድ ሰዓት ከ08 ደቂቃ በማጠናቀቅ ሲሆን ትውልደ ሶማሊያዊ እንግሊዛዊው ሞ ፋራህ በአንድ ሰዓት ከ09 ደቂቃ ሁለተኛ በመውጣት ውድድሩን ሲያጠናቅቅቅ አትሌት ኃይሌ ገብረ ሥላሴ ደግሞ ሶስተኛ በመሆን ውድድሩን አጠናቋል፡፡ እንደ ስፖርት ተንታኞች ከሆነ ኃይሌ ለቀነኒሳ ማሸነፍ ትልቁን ሚና ተጫውቷል። የቀነኒሳ ማሸነፍም ኢትዮጵያ ወደፊት በማራቶን ተተኪ አትሌቶችን እያገኘች መሆኑን የሚያሳይ መሆኑን አስተያየት ሰጪዎች ይናገራሉ።

በተመሳሳይ ዛሬ መስከረም 5 /2005 (ሴፕቴምበር 15 ቀን 2013) ዓ/ም የተካሄደው የሰሜን እንግሊዝ ታላቁ ግማሽ ማራቶን ሩጫ መሠረት ደፋርና ጥሩነሽ ዲባባ ሁለተኛና ሶስተኛ በመውጣት አሸንፈዋል። በዚህ የሴቶች ግማሽ ማራቶን ውድድር ኬንያዊቷ አትሌት ጀፕቶ አንደኛ ስትወጣ አትሌቷ ጅፕቶ ከአስር ዓመት በፊት በፓዉላ ራድክሊፍ የተያዘ የ1፡05፡40 ሰዓት የቦታው ሪከርድ ለመስበር 9 ሰከንድ ብቻ እንደቀራት ከሥፍራው የተገኘው መረጃ ያመለክታል። የዚህ ውድድር ያለፈው ዓመት አሸናፊ ኢትዮጵያዊቷ ጥሩነሽ ዲባባ ነበረች። በ5 ሺህ እና በ10 ሺ ሜትር በድል ያስጨፈሩን መሰረት እና ጥሩነሽ በዚህ የግማሽ ማራቶን ያገኙት ውጤት የሚያኮራ ነው።

እንኳን ደስ ያለን!!


ቀነኒሳ በቀለ ያሸነፈበት ቪድዮ – Video

ኃይሌ ሩትስ በሚኒያፖሊስ ቀለበት አሠረ

0
0

hailie roots

(ዘ-ሐበሻ) በሬጌ የሙዚቃ ስልት የሚታወቀው ድምጻዊ ኃይሌ ሩትስ በሚኒሶታ ትናንት ሴፕቴምበር 15 ቀን 2013 ዓ.ም ቀለበት አሰረ። ድምፃዊ ኃይለሚካኤል ጌትነት (ኃይሌ ሩትስ) ቀለበት ያሠረው ነዋሪነቷ ሚኒሶታ ውስጥ ከሆነችው ከወይዘሪት ነዋል ስምዖን ጋር መሆኑን ጨምሮ የደረሰን መረጃ ያመለከታል።
በዳውንታውን ሚኒያፖሊስ በተለምዶ “SEVEN Steakhouse” እየተባለ በሚጠራው ቦታ ቀለበቱን ያሠረው ድምፃዊ ሃይሌ ሩትስ ሠርጉን ኢትዮጵያ እንደሚያደርግ ይጠበቃል።

በዚህ የሠርግ ሥነ- ሥርዓት ላይ የዘ-ሐበሻ ዘጋቢዎች ለመገኘት ሄደው የነበረ ቢሆንም ከበሩ ጀምሮ ፎቶ ግራፍ ማንሳት ክልክል ነው የሚሉ ፖስተሮች በመለጠፋቸው አንዳችም ፎቶ ግራፍ ለማንሳስት አልቻልንም። በተጨማሪም በቀለበቱ ላይ የታደሙት ወገኖችም በስልካቸው ጭምር ፎቶ ግራፍ ማንሳት እንዳልቻሉም ለማወቅ ተችሏል። “ቺጌ” በሚል አልበሙ ታዋቂነትን ያተረፈው ኃይሌ ሩትስ በአንድ ወቅት በዘ-ሐበሻ ላይ በታተመው ቃለ ምልልሱ ላይ “እኔ ብዙ ግርግር አልፈልግም፤ ብዙ መታየትም አልወድም” ሲል መናገሩን ያስታወሱት ወገኖች ምናልባትም የቀለበቱ ፎቶ ግራፍ እንዳይነሳ የከለከለው በሚዲያዎች በኩል ስሙ እንዳይነሳ ይሆናል የሚሉ አስተየት ይሰጣሉ።

ሃይሌ ሩትስ በዘ-ሐበሻ ላይ በታተመው ቃለ ምልልሱ ላይ፡ “ጥያቄ፡- የቤተሰቦችህ ሁኔታ ምን ይመስላል? የት ተወለድክ? የት አደግክ? የት ተማርክ? ከቤተሰብ ያንተን ፈለግ የተከተለ አለ?” የሚል ጥያቄ ቀርቦለት “ዘጠኝ ወንድማማቾች ነን፡፡ ሁለት እህቶች አሉኝ፡፡ ከመጨረሻ ሁለተኛ ልጅ ነኝ፡፡ እናቴ በህይወት የለችም፡፡ አባቴ አለ፡፡ አባታችን ነው ያሳደገን፡፡ ያደግሁት እንግሊዝ ኤምባሲ አካባቢ ነው፡፡ አንደኛ ደረጃን ስላሴ ካቴድራል፤ ሁለተኛ ደረጃን ደግሞ ዳግማዊ ምኒልክ ነው የተማርኩት፡፡ ከዚያ በኋላ ትምህርት አልሆነኝም (ሳቅ)፡፡ እግርኳስ ተጨዋች ነበርኩ፤ እግርኳስ በጣም ነበር የምጫወተው፤ ከዚያ እርሱን ተውኩና ወደ ሙዚቃው ገባሁ፡፡
ሙዚቀኛ በዘሬም የለም፤ እኔ ብቻ ነኝ በድፍረት የወጣሁት፡፡ ለዚያ ነው በወቅቱ ሙዚቃ ስጀምር ተቸግሬ የነበረው፡፡ መግባባት አልነበረም፤ ቤተሰብ የሚፈልገው የሃይማኖት እና ሌላ ሌላውን ሙያ ስለነበር ይህን አይደግፉትም ነበር፡፡ እና በወቅቱ ችግር ነበር፡፡” ሲል መመለሱ ይታወሳል።

ከዚህ ቀደም በዘ-ሐበሻ ድረ ገጽ ላይ የታተመውን ቃለ ምልልስ ለማንበብ እዚህ ይጫኑ

መስከረም ሲጠባ አደይ ሲፈነዳ ……

0
0

 

ከይድነቃቸው ከበደ

(የሰማያዊ ፓርቲ የህግ ጉዳይ ኋላፊ)

Yidnakachewየዘመን መለወጫ ክብረ በዓል በየትኛውም አገር እንደ አገሩ ወግና ልማድ በድቅመት የሚከበር በዓል ነው፤በእኛ ኢትዮጵያዊያን ዘንድ ደግሞ ልማድና ወጋቻን እጅግ ከመጠንከሩ የተነሳ ለአዲስ ዓመት ወይም ለዘመን መለወጫ ክብረ በዓል ዝግጅታችንም ሆነ አከባበራችን እጅግ በጣም ጠንካራና ደስ የሚል ነው፡፡

አዲስ ዓመት የሁሉ ነገር መጀመሪያ ነው ለዚህም ነው ብዙ እቅዶቻችን ከመስከረም ወር የሚጀምረው፤ያቀድነው ነገር በዓመቱ መጨረሻ ሊሳካ ወይም ላይሳካ ይችል ይሆናል ቁም ነገሩ ግን በዓመቱ መጀመሪያ እስከ ዓመቱ መጨረሻ ለማሳካት የታሰበ እቅድ መኖሩ ነው፤ለእቅዱ አለመሳካት ውጫዊና ውስጣዊ ምክንያቶች ሊኖሩ ይችላሉ እነዚህን እንቃፋት የሆኑ ምክንያቶች ለይቶ ማወቅ በራሱ የእቀዱ አንድ አካል በማደረግ እንደገና ለመጪው አዲስ ዓመት ለተሸለ እቅድ ግባት ይሆናል፡፡

የዘንድሮ አዲስ ዓመት ከግለሰባዊ ፋይዳ በላይ አገራዊና ህዝባዊ የለውጥ ፋይዳ የበዛ እንደሚሆን ምልክቶቹ አብዝተው ይታያሉ፤እነዚህ ምልክቶች ከባለፈው ዓመት ለዘንድሮዎ የተሸጋገሩ የለውጥ ምልክቶች ናቸው፤በመሆኑም ለለውጥ የተነሳሳው ለወጥ ፈላጊ ለውጡኑ የሚያከሽፍበት አንዳችም ምክንያት ስለመኖሩ እጠራጠራለው ክሽፈት ቢያጋጥም እንኳን ወድቆ ለመነሳት ብዙ ጊዜ የሚባክን አይመስለኝም ፡፡

መውደቅ መነሳት ከሚንቀሳቀስ ነገር የሚጠበቅ ክስት ነው መንቀሳቀስ ደግሞ በሀገር ውስጥና በውጪ በሚገኙ አገር ወዳድ ኢትዮጵያዊያን፣ ፖለቲከኞች፣ በአይማኖት ተቋመት፣በሲቪክ ማህበራት እና በመሳሰሉት እንቅስቃሴው መሰልቸትና ድካም የማይታይበት ጠንካራ እንቅስቃሴ ነው፤ይህ እንቅስቃሴ ከባለፉት ወድቆ መነሳት እንቅስቃሴ ት/ት የተቀሰመበት ስለመሆኑ ከምልክቶቹ መካከል አንዱ ነው፡፡

በአገራችን ለለውጥ የሚገፋፉ ብዙ ምክንያቶች መኖራቸው የሚታወቅ ቢሆንም ከብዙ ምክንያቶች በዋንኝነት ትኩረትን የሚስቡት የለውጡን አይቀሪነት አሳበቂ ምክንያቶች ከሆኑት ውስጥ፡-

1ኛ. በዓለም ላይ ካሉ ታላላቅ እምነቶች መካከል ክርስትና እና እስልምና ዋንኞቹ ናቸው፤እነዚህን እምነቶች በመቀበል እኛ ኢትዮጵያዊያን ከቀዳሚዎቹ መካከል እንገኛለን ክርስትናን እና እስልምና እምነትን መቀበላችን ብቻ ሣይሆን የተቀበልነው እምነት ህግና ሥርዓት አክብሮ በማስከበር ወደር አይገኝልንም፡፡ይሁን እንጂ መንግስት በልማት ስም  የአምልኩ ቦታዎችን በመጋፋት ቤተ ክርስቲያንን ተዳፍሯል፤ይህ ነገር ተገቢ አይደለም ያሉ የሃይማኖት አባቶች ተደብድበዋል፣ተገለዋል እንዲሁም ከአገር ተሰደዋል፡፡

መንግስት በሃይማኖት ሃይመኖት በመንግስት ጣልቃ አይገባም የሚለውን ህገ-መንግስታዊ ድንጋጌ መንግስት በመጣስ በሙስሊም እምነት ዘው ብሎ በመግባት የእመንቱን መሪዎች እስከመምረጥ ደረጃ ተደርሷል፤ ይህን አይቶ ዝም አለማለት እስላማዊ ግዴታ እንደመወጠት የቆጠሩ እንቢ ለእምነቴ ያሉ በእስር እና በስቃይ ላይ ይገኛሉ፡፡    በእነዚህ ታላላቅ እምነቶች መንግስት እጁን በማስገባት የፖለቲካ ዓላማ ማስፈፀሚያ ለማድረግ ያልፈነቀለው ድንጋይ ምን አለ? በተለይ በሙስሊሞች ላይ እተየፈፀመ ያለው በደል እና በእምነቱ ተከተዮች የሙስሊም መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴዎች ላይ ያለጥፋታቸው በሐሰት በመወንጀል አሸባሪ ብሎ በእስር ማሰቃየቱ እጅን ጨብጦ ጥርሱን ነክሶ ያልተቆጨ ማነው ?

2ኛ. ኢትዮጵያ አገራችን የብዙ ሺህ ዓመት አኩሪ ታሪክ ያላት እና የተለያዩ –ን–ዎች የሚነገርባት ህዝቧ የቋንቋ ልዩነት ሣይገድበው አንዱ ከሌላው የተዋለደባት እጅግ ውብ እና ማራኪ –ን–፣ብህል ፣ልምድ ፣ወግ ፣አለባበስ እና አመጋገብ ወዘተ….. የሚታይባት ድንቅ አገራችን ናት፡፡ ይሁን እንጂ የኢህአዴግ መንግስት ይህ ቦታ የናተ አይደለም በማለት ዜጎችን በማፈናቀል ሀብትና ንብረት በማውደም ጎጠኝነትና ዘረኝነት በማስፋፋት ላይ ይገኛል፤እንዲህ አይነቱ አሳፋሪ ተግባር በአገራችን በአራቱም አቅጣጫ በዘመቻና በእቅድ በመንግስት የተፈፀመ ህገወጥ ተግባር ነው፡፡በመሆኑም ከኢትዮጵያዊነት በላይ መንደረኝነት እንዲነግስ በመንግስት እየተደረገ ያለው ዘመቻ ያላስቆጨው፣ ያላንገበገበው ማነው ? ይህን ቁጭቱን እና በደሉን ለመግለፅ ጊዜና አጋጣሚውን እየጠበቀ ያለው ስንቱ ነው ?

እኛ ኢትዮጵያዊያን በእድሜና በውቀታቸው ከፍ ላሉ ሰዎች ያለን ከበሬታ እጅግ የላቀ ነው ፤ለዚህም ነው ለሽምግልና ጉዳይ ቶሎ እጅ የምንሰጠው በሽምግልና ካጣነው ነገር በላይ ያተረፍነው የበዛ ነው ፡፡ ይሁን እንጂ የቆየውና ጠቃሚ የሽምግልና ወገና ሥርዓት በመጠበቅ የአፋር ፣ የኦሮሚያ ፣ የጋምጎፋ (ቆጫ ወረዳ) እና የሲዳማ የአገር ሽማግሌዎች በአካባቢያቸው ለታየው አስተዳዳሪያዊ ችግር መፍትሔ ለመሻት ከታችኛው የአስተዳደር አካል እስከ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ያደረጉት ጥረት ውጤት አልባ ነበር፤ ከምንምንም በላይ የሽምግልና ክብር በመጋፋት መንግስት ጠቃሚ የሆነውን ወግና ሥርዓት ለመናድ የሄደበት መንገድ ሽማግሌዎችንና የተወከሉበትን ማህበረሰብ ምን ያህል ነው ያስከፋው ?

3ኛ. ‹‹ በኑሮ ውድነት የጎበጠው ትከሻችን እረፍት ይሻል ›› ኑራችን አላምር ሲል መፈክራችን ማማሩ የሚገርም ነው ! ይህ መፈክር ሰማያዊ ፓርቲ በአዲስ አበባ ባካሄደው የተቃውሞ ሠልፍ ከፍ ብሎ የተሰማ ጥያቄ ነወ፤ እውነትም አብዛኛው ኢትዮጵያዊ የኑሮ ውድነት ትከሻውን ከማስጉበጥ አልፎ ህይወቱን እየነጠቀወ ነው፡፡ ባለ ሁለት ሃአዝ እድገት በመንግስት ተደጋግሞ የሚነገር አስማታዊ እድገት ምግብም መጠጥም አልሆን ብሎ በመንግስት የሚነገረው እድገትና የምንኖረው ሕይወት ሆድና ጀርባ ሆኖ አልገጥም እያለ ተቸግረናል፡፡

የስራ አጥነት ቁጥሩ በጣም የበዛ ነው፣ሰራተኛም ሰርቶ የሚከፈለው ወራዊ ደሞዝ ወሩን ሙሉ የሚያቆይ አይደልም፣ በኑሮ ውድነቱ ምክንያት 2.5 ሚሊዩን ዜጎች ለጎዳና ተዳዳሪነት መዳረጋቸው የመንግስት መስሪያ ቤት የሆነው የማህበራዊ ዋስትና ድርጅት ባስጠናው ጥናት መሰረት ይፋ አድረጎኃል፤ጎዳና ያልወጡ እቤታቸው ጎዳና የሆነባቸው ዜጎች ቤት ይቁጠራቸው፡፡

በመሆኑም እንዲህ አይነቱ ምስቅልቅል የበዛበት የኑሮ ውድነት ዋንኛው መንስሄ ብልሹ የመንግስት አስተዳደር ስለመሆኑ የእኛ መንገስትና ኑራችን ዋንኛ ማስረጃ ነው፤ስለሆነም እንዲህ አይነቱ ብልሹ የመንግስት አስተዳደር አቅፎና ደግፎ ይዞ የሚሄድ ጉልበትም ሆነ አንጀት ከወዴት ይምጣ ?

4ኛ. አሁን ያለው የአባገነን ሥርዓት የተረጋጋና ጉልበት አልባ መሆኑ ሌላኛው የለውጡን አይቀሪነት አሳበቂ ምክንያት ነው፡፡ ከእሳቸው ሞት በፊት ይታይ የነበረው የአንድ ሰው ፈላጭ ቆራጭነት ከእሳቸው ሞት በኃላ የስርዓቱ ፊት አውራሪዎች ከመብዛታቸውም በላይ በቡድን የተከፈሉና እኛ እናተ መባባላቸው ከጥጋባቸው በላይ የስልጣን ጥማታቸውን የሚያሳይ ነው፤ ግን በሁለት ሆዳሞች መሃል እህል ይደፋል እንጂ ማንም አይበላውም፡፡

ሌላው የስርዓቱ የፊት ሰዎች ከውስጣዊ ሹኩቻ ባለፍ በአደባባይ አንዱ ለሌላው በሙስና እና በስልጣን መባለግ ስም ማሰርና መክሰስ ሌላኛው አገር ጥሎ መሄድ መሳ ለመሳ እየተካሄደ ያለ ውስጣዊ ሹኩቻ ነው፤በእንዲ መልኩ በውስጥ የተወጠረው የአባገነን ስርዓት በተጠናከረ እና ሠላማዊ በሆነ ህዝባዊ ግፊት ፈንድቶ ውስጣዊ ሰንኮፉ የማይነቀልበት ምክንያት ምንድነው ?

5ኛ. ሐሳብን በነጻ የመያዝና የመግለጽ እንዲሁም የመደራጀት መብት ዓለም አቀፍ  እንዲሁም ሕገ መንግስታዊ መብት ነው፡፡በመሆኑም አንዱአለም አራጌ፣ ናትናሄል መኳንን፣ በቀለ ገራባ፣ ኦልባና ለሊሳ እና ሌሎችም የፖለቲካ እስረኞች እንደማንም ኢትዮጵያዊ የራሰቸው ኑሮ እና ህይወት ያላቸው ናቸው፤ ይሁን እንጂ ነፃነት እና ፍትህ ለነሱ ሁለተኛ ጉዳይ አይደለም የመጀመሪያ ጥያቄያቸው ነው ! ከራስ ወዳድነት አልፈው ይህ ጥያቄ የኛ ብቻ ሣይሆን የኢትዮጵያዊያን ጥያቄ ነው በማለት በአደባባይ ስለነፃነት እና ፍትህ የዘመሩ በዚህም አኩሪ ተግባራቸው በእኛ የኢትዮጵያዊያን ዘንድ ልዩ ቦታ የምንሰጣቸው ነን፡፡የታሰሩበት እና የሚሰቃዩበት ጉዳይ የኛም ጉዳይ ነው የሚሉ ቁጥራቸው መብዛቱ ሠላማዊ ትግሉ አባገነን ስርዓቱን የሚበላ እሳት መሆኑ ማሳያ ነው፡፡

ይህ በእንዲ እንዳለ  በአገር እና በህዝብ ላይ የሚፈፀም በደል ማቆም አለበት መንግስት እየወሰዳቸው ያለው እርምጃ የዜጎች ሰብአዊ እና ዲሞክራሳዊ መብቶችን የጣሱ ናቸው፤ በማለት ሃሳብን በነፃነት የመግለፅ መብታቸውን ተጠቅመው ከምንም በላይ የጋዜጠኝነት ስነ-ምግባር ጠብቀው ሚዛናዊ መረጃ ለእዝብ ያደረሱ ዓለም ዓቀፍ ተሸላሚ የሆኑ ጋዜጠኖች በእስር ላይ ይገኛሉ፡፡ ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ፣ እርዮት ዓለሙ እና ውብሸት ታዬ በስራቸው ዓለም ያደነቃቸው አድናቆቱም በሽልማት የታጀበ መሆኑ ለማናችንም ግልፅነው፡፡ይሁን እንጂ እነዚህ የዓለም ህዝብ ቆሞ ያጨበጨበላቸው ጋዜጠኞች አባገነኑ መንግስት በሽብርተኝነት ወንጅሎ በማሰር እያሰቃያቸው ይገኛል ፡፡ ይህ ስቃያቸው ያልተሰማው ማነው ? ከዚህ ስቃይ እንዲወጡ ምን ባደርግ ይሻላል እያልን እራሳችንን ያልጠየቅን ስንቶቻችን ነን ? በሆነውስ ነገር ያልተቆጨ ማነው ?

6ኛ. በውጪ የሚገኙ አገር ወዳድ ኢትዮጵያዊያን ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ተፅኖ ሌላው ለአባገነኑ ሥርዓት የእግር እስታ መሆን ነው፤ በውጪ የሚገኙ ዜጎች በአገር ውስጥ ለታየው ብሉሹ አስተዳደር ፊት ከመንሳት ባለፈ በተደራጀና በሚያስደንቅ ሁኔታ የሚያደርጉት እንቅስቃሴ ነው፡፡ እንቅስቃሴውም ከሌላው ጊዜ በተሸለ በኢኮኖሚ እና በፖለቲካው ስኬታማ መሆኑ የውጪ ጉዳይ ሚኒስትሩ በተለያየ ወቅት በሰጡት ቃለ ምልልስ እና መንግስት በሰጠው መግለጫ በውጪ በሚገኙ አገር ወዳድ ኢትዮጵያዊያን መንግስት መሸነፉን የሚያሳብቅ ነው፡፡

በመሆኑም ከላይ በማሳያነት የቀረቡ የለውጡ ግፊት ሃይል ከሆኑ ምክንያቶች ውስጥ የተጨለፈ ቢሆንም  በመንግስት የአስተዳደር ብሉሹነት ምክንያት ይህ አስተዳደር በቃኝ ለማለት ምክንያቱ ብዙ ነው፡፡ ስለሆነም መስከረም ሲጠባ አደይ ሲፈናድ ለውጥ ፈላጊ የፈለገውን ለውጥ ላለማጣት ከባለፈው ዓመታት ት/ት በመውሰድ በዘንድሩ አዲስ ዓመት ከግለሰባዊ ፋይዳ በላይ አገራዊና ህዝባዊ ለውጦች የምናይበት ዓመት ይሆናል፡፡

 

ሰማያዊ ፓርቲ የፊታችን እሁድ በአ.አ. የሚደረገው ሰልፍ በታቀደለት ጊዜ እንደሚካሄድ አስታወቀ

0
0

ከሰማያዊ ፓርቲ የተሰጠ ማብራሪያ

ሰማያዊ ፓርቲ ነሐሴ 26 ቀን 2005 ዓ.ም ሊያካሂደው የነበረው የተቃዉሞ ሰላማዊ ሰልፍ በመንግስት ታጣቂዎች ህገ ወጥ እርምጃ ከተደናቀፈ በኋላ ነሐሴ 3ዐ ቀን 2ዐዐ5 ዓ.ም በተፃፈ ደብዳቤ ፓርቲው መስከረም 12 ቀን 2ዐዐ6 ዓ.ም ሰላማዊ ሠልፍ እንደሚያደርግ ለአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ጽ/ቤት የሰላማዊ ሠልፍና ስብሰባ ማሣወቂያ ክፍል እንዲያውቀዉ አድርጓል፡፡ ይህንን ተከትሎ የሰላማዊ ሠልፍና ስብሰባ ማሣወቂያ ክፍል ጳጉሜ 1 ቀን 2ዐዐ5 ዓ.ም. በተጻፈ ደብዳቤ የሰለፉን ዓላማ፣ የሰልፉ ተሳታፊዎች የሚጓዙበትን መስመርና የሰልፉ መዳረሻ ከግንባታ ስራና ከፀጥታ ጥበቃ ጋር ያለውን ችግር አስመልክቶ ማብራሪያ እንደሚያስፈልግ በጠየቀዉ መሠረት፡-

blue party1ኛ. የሰልፉ ዓላማ፤
በህገ መንግሥቱ የተደነገጉት ሃሣብን በነፃነት የመግለፅ መብት እንዲከበር፣ዜጐች በሁሉም የኢትዮጵያ አካባቢዎች ተዘዋውሮ የመሥራትና ሀብት የማፍራት መብታቸው እንዲከበር፣ በህገ መንግሥቱ አንቀጽ 11፡3 በግልፅ የተደነገገው መንግሥት በኃይማኖት ጉዳይ ጣልቃ አይገባም ኃይማኖትም በመንግሥት ጉዳይ ጣልቃ አይገባም የሚለው ድንጋጌ እንዲከበር፣ መንግሥት የኑሮ ውድነትና ሥራ አጥነትን ለመቅረፍ የፖሊሲ ማሻሻያ እንዲያደርግ የሚሉትን ጥያቄዎች በሰላማዊ ሠልፍ መንግሥትን ለመጠየቅ መሆኑን፤

2ኛ. የሰልፉ ተሳታፊዎች የሚጓዙበትን መስመር
መነሻው ከፓርቲው ጽ/ቤት ግንፍሌ አካባቢ ተነስቶ በአራት ኪሎ ቱሪስት ሆቴል በኩል በአሮጌው ቄራ በአምባሳደር ቴአትር አልፎ መስቀል አደባባይ ሲሆን፣ በዚህ መንገድ ላይ ምንም ዓይነት የግንባታ ሥራ የሌለበትና ሠልፉ የሚደረገውም እሁድ ከጥዋቱ 3፡ዐዐ-7፡00 ሰዓት ባለው የእረፍት ቀን በመሆኑ በዕለቱ ምንም ዓይነት የመንግሥት ሥራና የትራፊክ መጨናነቅ የሌለበትና መድረሻ ቦታችንም መስቀል አደባባይ ከቅርብ ቀናት በፊት በኃይማኖት ተቋማት አስተባባሪነት ሠልፍ የተደረገበት መሆኑና ወደፊትም መስከረም 12 ቀን ከሚደረገው ሠልፍ አንድ ሳምንት ባነሰ ጊዜ ውስጥ ከሁሉም ማዕዘናት በሚመጡ ምዕመናን የመስቀል በዓል የሚከበርበት ቦታ መሆኑን ጳጉሜ 04 ቀን 2005 ዓ.ም በፃፍነው ደብዳቤ አብራርተናል፡፡

የሰላማዊ ሰልፍና ሕዝባዊ ስብሰባ ሥነ ሥርዓት አዋጅ ቁጥር 3/1987 አንቀፅ 6 ቁጥር 2 “የከተማው አስተዳደር ጽ/ቤት በዚህ አዋጁ አንቀፅ 6 ንዑስ አንቀፅ 1 የተመለከቱትን በማገናዘብ ሰላማዊ ሰልፉ በሌላ ጊዜ ወይም በሌላ ስፍራ ቢደረግ ይሻላል የሚል አስተያት ካለው ምክንያቱን በመግለፅ ይህንኑ ጥያቄው በደረሰው በ12 ሰዓት ውስጥ በጽሑፍ ለአዘጋጁ የማሳወቅ ኃላፊነት አለበት፡፡ ሆኖም የከተማው አስተዳደር ጽ/ቤት ሰላማዊ ሰልፉ ምንጊዜም በየትኛውም ቦታ ሊካሔድ አይችልም ማለት አይችልም” በሚለው መሰረት የእዉቅና ጥያቄ የቀረበለት አካል በፅሁፍ በ12 ሰዓት ውስጥ መልስ የመስጠት ግዴታ ቢኖርበትም እስካሁን የተሰጠ ምላሽ የለም፡፡

ፓርቲያችን በሕግ የሚጠበቅበትን ለሚመለከተዉ አካል የማሳወቅ ግዴታ በአግባቡ ስለተወጣና ለሰልፉም የሚያስፈልጉ ስራዎች እየተከናወኑ በመሆኑ መስከረም 12 ቀን 2006 ዓ.ም በታቀደው መሰረት ያካሂዳል፡፡ በመሆኑም በዚህ ታላቅ ሰላማዊ ሰልፍ የምናነሳቸው ጥያቄዎች ምላሽ እንዲያገኙ የፖለቲካ ፓርቲዎች የሲቪክ ማሕበራትና ዜጎች በአጠቃላይ በሰልፉ ላይ በመሳተፍ የዜግነት ድርሻቸውን እንዲወጡ ፓርቲያችን ጥሪውን ያቀርባል፡፡

በመጨረሻም ሰላማዊ ሰልፉን በመቆጣጠርና የሕዝብን ሰላምና ፀጥታ የሚያውክን ሁኔታ በማስወገድ የሰላማዊ ሰልፈኞች መብቶችን ለመጠበቅ የፖሊስና የፀጥታ ኃይሎች በአዋጁ ቁጥር 3/1987 የተሰጣቸውን ኃላፊነትና ተግባር በአግባቡ እንዲያከናውኑ እናሳስባለን፡፡

መስከረም 6 ቀን 2006 ዓ.ም.

አዲስ አበባ

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የግል ባንኮችን አካውንት አገደ

0
0

ዳዊት ታዬ /ሪፖርተር 

eth Bankየባንክ ኢንዱስትሪ ውስጥ የአንበሳውን ድርሻ በያዘው መንግሥታዊው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ውስጥ አካውንት ያላቸው የግል ባንኮች አካውንታቸውን እንዳያንቀሳቅሱ ታገዱ፡፡

ከአንዳንድ የግል ባንኮች የተገኘው መረጃ እንደሚያመለክተው፣ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ውስጥ ያላቸውን አካውንት እንዳያንቀሳቅሱ የተገለጸላቸው፣ አካውንታቸው ባለበት ቅርንጫፍ ሥራ አስኪያጅ በኩል በተጻፈ ደብዳቤ ነው፡፡

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ይህንን ዕርምጃ ለመውሰድ የተገደደበት ምክንያት ግልጽ ባይሆንም፣ ከሰኞ መስከረም 6 ቀን 2005 ዓ.ም. ጀምሮ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ውስጥ የነበራቸውን አካውንት ማንቀሳቀስ የማይችሉ መሆኑ እንደተገለጸላቸው ታውቋል፡፡

ጉዳዩን በተመለከተ ያነጋገርናቸው የግል ባንኮች ኃላፊዎች እንደጠቆሙት፣ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ዕርምጃ ያልተጠበቀ እንደሆነባቸው ነው፡፡ ‹‹ሆኖም የእኛን የተወዳዳሪዎቹን አካውንት እንዳይንቀሳቀስ ሲያደርግ ቢያንስ ምክንያቱን ሊገልጽ ይገባ ነበር፤›› ይላሉ፡፡ የግል ባንኮቹ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ውስጥ አካውንት የከፈቱበት ዋነኛ ዓላማ አንዳንድ ክፍያዎችን በቀጥታ ከዚያ ለመክፈል እንዲያስችላቸው እንጂ ሌላ ዓላማ የሌለው መሆኑን የግል ባንኮች ኃላፊዎች ያስረዳሉ፡፡

አንድ ባንክ በሌላ ባንክ ውስጥ አካውንት ሊከፍት የሚችለው በሥራ ውስጥ የሚያጋጥሙ ክፍያዎችን በቀላሉ ለመፈጸምና የተቀላጠፈ አገልግሎት ለመስጠት ታስቦ ነው በማለት የሚያስረዱት የግል ባንኮች ኃላፊዎች፣ ይህ በባንክ ኢንዱስትሪ ውስጥ የተለመደ አሠራር ቢሆንም የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ወደዚህ ዕርምጃ መግባቱ እንቆቅልሽ እንደሆነባቸው አስረድተዋል፡፡

በአሁኑ ወቅት 19 ባንኮች በሥራ ላይ ሲሆኑ፣ ሦስቱ የመንግሥት 16ቱ ደግሞ የግል ናቸው፡፡ የግሎቹም ሆነ የመንግሥት ባንኮች በጥምረት የሚያስተሳስራቸው የኢትዮጵያ ባንኮች ማኅበር ሲሆን፣ አሁን የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የወሰደውን ዕርምጃ በማኅበራቸው በኩል ለመነጋገር ሐሳብ ያላቸው መሆኑንም የተገኘው መረጃ ያስረዳል፡፡

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አካውንታቸው እንዳይንቀሳቀስ ወሰነ ማለት ግን በአካውንታቸው ውስጥ ያለውን ገንዘብ ያግዳል ማለት እንዳልሆነ ተጠቅሷል፡፡

አንዳንዶቹ የግል ባንኮች አካውንቱ ለምን እንዲታገድ እንደተደረገ ላቀረቡት ጥያቄ ማብራሪያ ባለማግኘታቸው በሁኔታው ማዘናቸውን ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አንዳንድ ኃላፊዎችን ለማነጋገር የተደረገው ሙከራ ካለመሳካቱም በላይ፣ በሞባይል ስልካቸው በጽሑፍና በድምፅ የተላለፈላቸውን ጥያቄ ለመመለስ ፈቃደኛ ሳይሆኑ ቀርተዋል፡፡

“የኢትዮጵያ ሕዝብ እንዲያውቅልኝ የምፈልገው ነገር አለ”ድምፃዊ ደሳለኝ ብርሃኑ (Video)

0
0

“የኢትዮጵያ ሕዝብ እንዲያውቅልኝ የምፈልገው ነገር አለ” ድምፃዊ ደሳለኝ ብርሃኑ (Video)(ዘ-ሐበሻ) ነዋሪነቱን በሰሜን አሜሪካ ያደረገው ድምፃዊ ደሳለኝ ብርሃኑ አንድን ዘፈን እርሱ እና ሚካኤል ንጉሱ የተባለ ድምፃዊ መጫወታቸውን ተከትሎ የኢትዮጵያ ሕዝብ እንዲያውቅልኝ የምፈልገው አለ በሚል ዘፈኑ የርሱ መሆኑን አስታወቀ። ዜማና ግጥሙን ለሁለታችንም የሰጠን ኤፍሬም አበበ የተባለው ደራሲ ነው ያለው ድምፃዊ ደሳለኝ ደራሲው ዘፈኑን ለሌላ ድምፃዊ እንደሰጠው እያወቀ ሃገር ቤት ርቄ መኖሬን ከግምት በማስገባት ወንጀል ፈጽሞብኛል ብሏል። ቃለ ምልልሱን በቪዲዮ ይመልከቱት።

የቤተመንግስት ደህንነት ሃላፊ ተነሱ (ከኢየሩሳሌም አርአያ)

0
0

ከኢየሩሳሌም አርአያ

Azeb investment ethiopiaየቤተ-መንግስት የደህንነት ጥበቃ ዋና ሃላፊ ሆነው ሲያገለግሉ የቆዩት የሕወሐት አባል አቶ ጌታቸው ተፈሪ ከስልጣናቸው መነሳታቸውን ምንጮች አስታወቁ። አቶ ጌታቸው ቀደም ሲል በክልል 14 ፖሊስ ኮሚሽን የደሕንነት ልዩ ተወርዋሪ ሃይል ሃላፊ ተደርገው ሲያገለግሉ መቆየታቸውን የጠቆሙት ምንጮች፣ ከዚያም ወደ ቤተ መንግስት ተዛውረው መመደባቸውንና በተጨማሪ የአገር ውስጥ ደህንነት ምክትል ሃላፊ በመሆን ከአቶ ወ/ስላሴ ወ/ሚካኤል ጋር ሲሰሩ መቆየታቸውን አስረድተዋል። የአቶ መለስና ወ/ሮ አዜብ የቅርብ ሰው የሆኑት አቶ ጌታቸው ተፈሪ በነበራቸው ታማኝነት የቤተመንግስት የደህንነት ሃላፊ ተደርገው በአቶ መለስ ተመርጠው እንደተሾሙ ያስታወሱት ምንጮች፣ በማያያዝም እስከ 1994ዓ.ም የቤተመንግስት የደህንነት ጥበቃ በሃላፊነት ሲመሩ የቆዩት አቶ ዘርኡ መለስ በወቅቱ ከአቶ መለስ ጋር በፈጠሩት የፖለቲካ ልይነት ምክንያት ካዛንቺስ አካባቢ በሚገኘው የቀድሞ “ኮከብ ሬስቶራንት” የአሁኑ “ሚልክ ሃውስ” መኖሪያ ሕንፃ አንደኛ ፎቅ ቤታቸው ውስጥ አንገታቸው በስለት ታርዶና በድናቸው ተበላሽቶ መገኘቱን አመልክተዋል። ይህን አሰቃቂ ግድያ ያከናወነው አሁን በእስር ቤት የሚገኘው የቀድሞ አገር ውስጥ ደህንነት ሃላፊና የአቶ መለስ ቀኝ እጅ ወ/ስላሴ ወ/ሚካኤል መሆኑን ምንጮቹ አጋልጠዋል።

አቶ ጌታቸው ተፈሪ ከስልጣን እንዲነሱ የተደረገው በደህንነት ዋና ሹም አቶ ጌታቸው አሰፋ ትእዛዝ መሆኑን ያመለከቱት ምንጮች፣ በአሁኑ ወቅት በምን ሁኔታ ላይ እንደሚገኙ እንደማይታወቅ ጠቁመዋል። አቶ ጌታቸው ተፈሪ — የወ/ስላሴ መታሰር ቅር ሳያሰኛቸው እንዳልቀረና በተጨማሪም የነአዜብ ቡድን ደጋፊ መሆናቸውን ምንጮቹ አመልክተዋል።
በሌላ በኩል የኢ.ኤም.ኤፍ ምንጮች ቀደም ብለው እንደገለጹት፤ ባለፈው አመት የቀድሞው ጠቅላይ ሚንስትር መለስ ዜናዊ ከሞቱ በኋላ “ቤተ መንግስቱን አንጠብቅም” ብለው ንዝህላልነት ካሳዩት መሃል እኚሁ የቤተ መንግስት ጥበቃ ሃላፊ ጌታቸው ተፈሪ አንዱ ነበሩ። በተለይም አዲሱ ጠ/ሚንስትር አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ ከገቡ በኋላ የቤተ መንግስቱ ጥበቃ እንዲላላ ከማድረግ አልፈው፤ ለአዲሱ ጠቅላይ ሚንስትር አክብሮት የማይሰጡ ሰው እንደነበሩ ይታወቃል።


(Breaking News) 4 የአየር ኃይል አብራሪዎችና አስተማሪዎች ግንቦት 7ን ተቀላቀሉ

0
0

የኢትዮጵያ  ሚግ-23 (ፎቶ ፋይል)

የኢትዮጵያ ሚግ-23 (ፎቶ ፋይል)

(ዘ-ሐበሻ) በቅርቡ በሱማሌያና በዳርፉር የሰላም ማስከበር ሥራ ላይ ተሰማርተው የነበሩ 4 የኢትዮጵያ ዓየር ኃይል አብራሪዎች እና የበረራ አስተማሪዎች የግንቦት 7 ንቅናቄን መቀላቀላቸውን ኢሳት በሰበር ዜናው ዘገበ።

የሕወሓት/ኢህ አዴግን አስተዳደር ከድተው ግንቦት 7ትን የተቀላቀሉት እነዚህ የአየር ኃይል ከፍተኛ የጦር መኮንኖች 2ቱ ሻለቃ እንዲሁም ካፒቴኖች እንደሆኑ ስማቸውም እንደሚከተለው ነው…

1፦ ካፒቴን አክሊሉ መዘነ፣
2፦ ካፒቴን ጥላሁን ቱፋ፣
3፦ ካፒቴን ጌቱ ወርቁና
4፦ ካፒቴን ቢንአም ግዛው

አና ጎመሽ –ርዕዮትና እስክንድር “የኅሊና እሥረኞች ናቸው” አሉ

0
0

 

hana

ለያዝነው የአውሮፓ 2013 ዓ.ም የአውሮፓ ፓርላማ የሳኻሮቭ ሽልማት ሁለት ኢትዮጵያዊያንን ጨምሮ ሰባት ዕጩዎች ቀርበዋል፡፡
ለያዝነው የአውሮፓ 2013 ዓ.ም የአውሮፓ ፓርላማ የሳኻሮቭ ሽልማት ሁለት ኢትዮጵያዊያንን ጨምሮ ሰባት ዕጩዎች ቀርበዋል፡፡

ሽልማቱ ለሃሣብ ነፃነት ለሚታገሉና ለታገሉ የሚሰጥ የአውሮፓ ፓርላማ ዓመታዊ ክንዋኔ ነው፡፡

ኢትዮጵያዊያኑን ዕጩዎች ርዕዮት ዓለሙንና እስክንድር ነጋን ለሽልማት ካቀረቡት አርባ የአውሮፓ ፓርላማ አባላት አንዷ የፓርላማው አባል፣ እንዲሁም የውጭ ጉዳዮች ኮሚቴው እና የሰብዓዊ መብቶች ንዑስ ኮሚቴ አባል የሆኑት አና ጎመሽ ይገኙበታል፡፡

ርዕዮት ዓለሙርዕዮት ዓለሙ


በአሁኑ ምርጫ ርዕዮት እና እስክንድር ቁጥራቸው ወደ 12 ከሚደርስ ከመላው ዓለም ከተጠቆሙ ሰዎች መካከል ወደ ሰባቱ አጭር ዝርዝር የገቡ መሆኑን ሚስ ጎመሽ ጠቁመው ፓርላማው የፊታችን ጥቅምት ውስጥ በሚያደርገው የተሟላ ስብሰባው ላይ አንዱ ለሽልማቱ በድምፅ እንደሚወጣ አመልክተዋል፡፡

እስክንድርና ርዕዮት የተመረጡት ፓርላማው ባወጣው መስፈርት መሠረት የሚያደርጉት ትግል የሃገራቸው ዴሞክራሲ፣ ነፃነትና ፍትህ የለው አስተዋዖ ተመዝኖ መሆኑንም ሚስ ጎመሽ ገልፀዋል፡፡

እስክንድር ነጋእስክንድር ነጋ

“እነዚህ ሰዎች እውነተኛ የሰብዓዊ መብቶች ታጋዮች ናቸው – ያሉት አና ጎመሽ ሁለቱ የኅሊና እሥረኞች ብቻ ሣይሆኑ በኢትዮጵያና በመላ አፍሪካም ለነፃነት፣ ለዴሞክራሲ፣ ለሕግ የበላይነት ለሚታገሉ ሁሉም ደወል ወይም መታያ ናቸው” ብለዋል፡፡

የያዝነው የአውሮፓ ዓመት የሃሣብ ነፃነት የሳኻሮቭ ሽልማት ዕጩዎች ስሞች ለውጭ ጉዳዮች እና የልማት ኮሚቴዎቹ ጥምር ስብሰባ መቅረባቸውን የአውሮፓ ፓርላማ ያስታወቀው ከትናንት በስተያ ሰኞ ነበር፡፡

በፓርላማው መግለጫ መሠረት ፓኪስታናዊቷ ማላላ ዩሳፍዛይ፣ አሜሪካዊው ኤድዋርድ ስኖውደን፣ ኢትዮጵያዊያኑ ርዕዮት ዓለሙ እና እስክንድር ነጋ፣ ቤላሩሲያዊያኑ አሌስ ቢያላትስኪ፣ ኤድዋርድ ላባዉ እና ማኮላ ስታትኬቪች በመላ የሃገሪቱ የፖለቲካ እሥረኞች ስም፣ ሩሲያዊው ሚኻይል ኾርዶቭስኪ፣ የቱርኩ “የቆመ ሰው” በሚል መጠሪያ የተጀመረው በቱርክ መንግሥቱ ላይ አፍጣጭ የታክሲም አደባባይ ተቃዋሚዎች ንቅናቄ የመጀመሪያው ተሰላፊ ኤርዶም ግዩንድዩዝ፣ የሲኤንኤን ቴሌቪዥን አውታር “ፍሪደም ፕሮጀክት (የነፃነት ፕሮጀክት)፡- ዘመነኛውን ባርነት ማብቃት” የሚባለው ፕሮግራም ናቸው፡፡

Source VOA

አንድነት መስከረም 19 በጠራው ሰላማዊ ሰልፍ ላይ ግማሽ ሚሊዮን ሕዝብ ይወጣል አለ –መኢአድም በሰልፉ ላይ ንቁ ተሳትፎ አደርጋለሁ ብሏል

0
0

በዘሪሁን ሙሉጌታ – ሰንደቅ

sept 19አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) ከ33ቱ ፓርቲዎች ጋር በጋራ በመሆን በመጪው መስከረም 19 ቀን 2006 ዓ.ም በመስቀል አደባባይ በጠራው ሰላማዊ ሰልፍ ላይ ግማሽ ሚሊዮን ሕዝብ እንደሚወጣ አስታወቀ። የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ) በበኩሉ ሰልፉ እንዲሳካ ከሰልፉ ዋና አስተባባሪ አንድነት ፓርቲ ባልተናነሰ ሁኔታ ንቁ ተሳታፊ እንደሚሆን ገልጿል።

የአንድነት ፓርቲ የጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አስራት ጣሴ እና የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት (መኢአድ) ሊቀመንበር አቶ አበባው መሐሪ ለሰንደቅ ጋዜጣ እንደገለፁት ሰላማዊ ሰልፉ ዋና ዓላማ ህገ-መንግስታዊ ጥሰትን መቃወምና መንግስትን ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ወደ ድርድር ለማምጣት ያለመ መሆኑን ገልፀዋል።

ሰልፉን በዋናነት እያስተባበረ ያለው አንድነት ፓርቲ ለአዲስ አበባ አስተዳደር የሰላማዊ ሰልፍና የህዝባዊ ስብሰባ ማሳወቂያ ክፍል ባቀረበው ቅጽ ላይ በሰላማዊ ሰልፉ ላይ በግምት ግማሽ ሚሊዮን (500ሺህ) ሰው እንደሚገኝ ይፋ አድርጓል። በሰልፉ ላይ መጠሪያቸውን 33 ያደረጉ ወደ 23 የሚሆኑ ፓርቲዎች ተሳታፊ እንደሚሆኑ ተገልጿል።
ቀደም ሲል የአንድነት ፓርቲ በሀገሪቱ ልዩ ልዩ ከተሞች ለሦስት ወራት ያህል ‘‘የሚሊዮኖች ድምፅ ለነፃነት’’ በሚል ርዕስ ሰላማዊ ሰልፎች ሲያካሂድ ቆይቷል። ከሕዝባዊ ንቅናቄው ዘመቻ መካከል የፀረ-ሽብር ህጉ ይሰረዝ የሚለው ይገኝበታል። ፓርቲው ይህንኑ ዘመቻ ማድረጉንም ተከትሎ የኢትዮጵያ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅት በርዕሰ ጉዳዩ ላይ ፓርቲዎችን ማከራከሩ አይዘነጋም።

በመጪው መስከረም 19 ቀን 2006 ዓ.ም በሚካሄደው ሰልፍ ላይ ሁሉም ፓርቲዎችን የጋራ መግባባት በደረሱበት ‘‘ህገ-መንግስታዊ ጥሰትን መቃወም’’ የሚል ጥቅል ሃሳብን በማንገብ፣ የፀረ-ሽብር ህጉና ሌሎች አፋኝ ሕጎች እንዲሰረዙ፣ የህሊና እስረኞች እንዲፈቱ፣ የተፈናቀሉ ዜጎች ወደ ቄዬአቸው እንዲመለሱ፣ የሃይማኖት ነፃነት እንዲከበርና የኑሮ ውድነት እና የስራ አጥነት ጥያቄዎች በጎላ መንገድ በሰልፉ ላይ እንደሚንፀባረቁ ከአቶ አስራትና ከአቶ አበባው ገለፃ መረዳት ተችሏል።

‘‘የኢህአዴግ አባል መሆን ከኢትዮጵያዊ ዜግነት በላይ የሆነበት ጊዜ ላይ ደርሰናል’’ ያሉት አቶ አስራት፤ ኢህአዴግ አባል ያልሆነ ብዙሃኑ የሙሉ ዜግነት መብቱን እየተነፈገ ነው ብለዋል። ይህ ሁሉ የሚያሳየው በሀገሪቱ የሕግ የበላይነት ጠፍቶ ኢ-ህገመንግስታዊነት መስፈኑን የሚያረጋግጥ በመሆኑ፤ ለህግ የበላይነት ለህገ መንግስታዊነት ክብር የሚሰጥ የከተማዋና የአካባቢዋ ህብረተሰብ በሰልፉ ላይ በመውጣት ተቃውሞውን እንዲያሳይ ሲሉ ጥሪ አስተላልፈዋል።

የመኢአድ ፕሬዝዳንት ፓርቲያቸው ከ33ቱ ፓርቲዎች ጋር በመሆን ከዚህ ቀደም በመኢአድ ጽ/ቤት ሕዝባዊ ስብሰባ ማስተባበሩን በማስታወስ መስከረም 19 ቀን በተጠራው ሰልፍ ላይ መላ አባሎቹና መዋቅሩን በማንቀሳቀስ በሰልፉ ላይ በዝግጅት ላይ መሆኑን ተናግረዋል።

የሰልፉ አላማ ህብረተሰቡ ያለበትን የፖለቲካ፣ የኢኮኖሚ፣ ማህበራዊና ሃይማኖታዊ ችግሮች ገደባቸው እያለፉ መሆኑን በገሃድ የሚያሳይበትና መንግስትም ከገባበት ኢ-ህገመንግስታዊ አካሄድ ቆም ብሎ ወደ ውይይት እንዲመጣ ለማስገደድ እንደሆነም ከፓርቲ አመራሮቹ ገለፃ መረዳት ተችሏል።

ሰልፉን ለማስተባበርና ስኬታማ ለማድረግ በአንድነት በኩል ልዩ ግብረሃይል መቋቋሙን የጠቀሱት አቶ አስራት፤ ሕዝቡም ያለአንዳች ማወላወል ወደ አደባባይ ወጥቶ ተቃውሞውን እንደሚያሳይም እምነታቸውን ገልፀዋል። ከሰልፉ በኋላ መንግስትና ተቃዋሚዎች በጋዜጣና በሬዲዮ የሚያደርጉትን የአሉባልታ ዘመቻ በማቆም ወደ ህጋዊና በሁሉም ወገኖች ተአማኒነት ወደአለው የውይይት መድረክ ይመጣሉ የሚል እምነት አለኝ ብለዋል።

“መንግስት አንድነት ሰላማዊ ሰልፍ በጠራበት ዕለት በተመሳሳይ በየቀበሌው ስብሰባ መጥራቱን እንዲሁም በቅርቡ ከሰማይ ወርዷል የተባለ መስቀል በአቃቂ ክፍለ ከተማ በሚገኘው የገብርኤል ቤተክርስቲያን በዕለቱ ሄዶ እንዲያይ መደረጉ በሰልፉ ላይ ህብረተሰቡ እንዳይገኝ ከወዲሁ የሚደረግ ጥረት ቢሆንም በእኛ በኩል ህብረተሰቡ ያለበትን አንገብጋቢ ችግር ስለሚገነዘብ ሰልፉ ላይ ከመገኘት ወደኋላ አይልም። መንግስት ትንንሽ ምክንያቶችን ሰበብ በማድረግ መሰናክል ለመፍጠር ቢሞክርም የሰልፉ አላማ ይመታል” ሲሉ አቶ አስራት ገልፀዋል።

ለአርቲስት ታማኝ በየነና ለሻምበል በላይነህ በእስራኤል የተደረገላቸው የጀግና አቀባበል ቪድዮ

“አሜሪካን ሃገር 6 ጊዜ ለመምጣት ሞክሬ እንደ ያሬድ በ7ኛው ተሳካልኝ”–ድምፃዊ ፋሲል ደመወዝ

0
0

“አሜሪካን ሃገር 6 ጊዜ ለመምጣት ሞክሬ እንደ ያሬድ በ7ኛው ተሳካልኝ” – ድምፃዊ ፋሲል ደመወዝ(ዘ-ሐበሻ) “አለው ነገር” በሚለው ዘፈኑ ከመንግስት ከፍተኛ ድብደባ ደርሶበት የነበረው የባህል ድምፃዊው ፋሲል ደመወዝ አሜሪካ ገብቷል። ድምፃዊው ይሁኔ በላይ በዋሽንግተን ዲሲ ከሚያሳትመው ባውዛ ጋዜጣ ጋር ባደረገው ቃለ ምልልስ “አሜሪካን ሃገር 6 ጊዜ ለመምጣት ሞክሬ ባይሳካልኝም እንደ [ቅዱስ] ያሬድ በሰባተኛው ተሳካልኝ” ብሏል። ፋሲል ከባውዛ ጋር በቪድዮ ባደረገው ቃለ ምልልስ አስቂኝ ገጠመኞቹንም አካፍሏል – የዘ-ሐበሻ ተከታዮችም እንድትካፈሉት አቅርበነዋል።

Viewing all 15006 articles
Browse latest View live