Quantcast
Channel: Ethiopian News | ዘ-ሐበሻ | Latest News Provider | News For All
Viewing all 15006 articles
Browse latest View live

አዲስ አበባን የቀይ አበባ ፌስቲቫል ያስመሰላት ኮካ ኮላ የጫነ መኪና አደጋ (ይናገራል ፎቶ)

0
0

coca cola

ይህን ፎቶ ግራፍ በሶሻል ሚዲያ ላይ የለቀቀው ፋሲል ተስፋዬ ነው። አንዳንድ ፎቶውን የተመለከቱ ሰዎች በ አዲስ አበባ ሁለት ጊዜ ቫለንታይን ደይ መከበር ጀመረ ወይ ሲሉ ተገርመዋል። ይህ የምትመለከቱት ኮልፌ አካባቢ ዛሬ የደረሰ አደጋ ነው። አደጋው ኮካ ኮላ የጫነ ከባድ ተሽከርካሪ ከነተሳቢው ተገልብጦ የጫነው የኮካኮላ ጠርሙስና የጠርሙስ መያዣው መንገዱን አጥለቅልቆት ነው። አደጋው የደረሰው ኮልፌ አካባቢ ነው።

The post አዲስ አበባን የቀይ አበባ ፌስቲቫል ያስመሰላት ኮካ ኮላ የጫነ መኪና አደጋ (ይናገራል ፎቶ) appeared first on Zehabesha Amharic.


«የእሣት ልጅ አመድ» የሆነው የዘመኑ ኢትዮጵያዊ ታሪካዊ ማንነቱን ያስከብር! –ሞረሽ ወገኔ የዐማራ ድርጅት

0
0

ሞረሽ ወገኔ የዐማራ ድርጅት             ሐሙስ ሚያዝያ ፳፯ ቀን ፪ሺህ፰  ዓ.ም.         ቅፅ ፬ ፣ ቁጥር ፲፬

 

 

ከዛሬ ሰማኒያ ዓመታት በፊት የነበሩት ኢትዮጵያውያን አባቶቻችን እና እናቶቻችን፣ ከትግራይ እና ከኤርትራ ምድር በበቀሉ ባንዶች አጋዥነት በፋሽስት ጣሊያኖች ጦር ማይጨው ላይ ድል ሲመቱ «እሺ፣ አሜን፣ እንገዛለን» ብለው እጃቸውን አጣጥፈው አልተቀመጡም። ራሣቸው ፋሽስቶችም እንዳመኑት፥ በተለይ በሰሜን ሸዋ፣ በጎጃም፣ በጎንደር፣ በወሎ፣ በጉራጌ፣ በጅባት እና ሜጫ እንዲሁም በሌሎች የኢትዮጵያ ክፍሎች የነበሩት አርበኞች በመረጧቸው የጎበዝ አለቆቻቸው እየተመሩ፣ ለአምሥት ዓመታት የፋሽስት ጣሊያንን ጦር ከእነ ባንዳ ግሣንግሱ መውጫ መግቢያ አሣጥተውታል። ከዚያም ከየካቲት 1933 ዓም ጀምረው ጀግኖች አርበኞቻችን ባደረጉት የተቀነባበረ የጥቃት ዘመቻ ልክ የዛሬ 75 ዓመት ሚያዝያ 27 ቀን 1933 ዓም በቀዳማዊ ኃይለሥላሤ መሪነት በድል አድራጊነት ዋና ከተማችንን አዲስ አበባን ለመቆጣጠር በቅተዋል። ሆኖም ዛሬ ላይ ሆነን ስናየው ያ ሁሉ መስዋዕትነት ያስገኘልንን ብሔራዊ ክብር እና ልዕልና እንዲህ አሽቀንጥረን እንድንጥል ያደረገንን ምክንያት ለመገንዘብ ትልቅ እንቆቅልሽ ይሆንብናል።

Moresh

የአምሥቱ ዓመት የፋሽስት ኢጣሊያ ወረራ በአገራችን በኢትዮጵያ ላይ ታላቅ የትውልድ ስብራትን ፈጥሮ አልፏል። ብዙ ጀግኖች አርበኞቻችን መሥዋዕት ሆነውብናል። በተቃራኒው ደግሞ ለፋሽስት ጣሊያኖች በባንዳነት ያገለገሉ አያሌ ከሃዲዎች ተፈልፍለዋል። በመሆኑም ፋሽስት ጣሊያኖች በጀግኖች አርበኞቻችን ከፍተኛ ተጋድሎ ከኢትዮጵያ ምድር ተጠራርገው ቢወጡም፣ እነርሱን በባንዳነት ሲያገለግሉ የነበሩት የእናት ጡት ነካሾች ግን ተንሠራፍተው ለመኖር በቅተዋል። ለዚህም የረዳቸው በተለይ ቀዳማዊ ኃይለሥላሤ ሥልጣናቸውን ለማደላደል ሲሉ በአገሪቱ የመንግሥት መዋቅር ውስጥ አብዛኞቹን የጣሊያን ሎሌ ባንዶች በመሾማቸው ነው። በሚያሣፍር ሁኔታ ንጉሠ-ነገሥቱ ይባስ ብለው አርበኞችን እያደኑ በእሥር፣ አልፎም በግድያ ቀጧቸው። የአርበኞችን ቤተሰቦች አጎሣቆሉ። በተቃራኒው የባንዶች ልጆች በምርጥ ምርጥ የውጭ አገር ትምህርት ቤቶች እና ዩኒቨርሲቲዎች እንዲማሩ አደረጉ። የተዘረጋውም ሥርዓተ-ትምህርት ተተኪውን ትውልድ ስለአገሩ እንዲያውቅ ሣይሆን የምዕራቡን ሥልጣኔ የበላይነት እንዲቀበል የሚሰብክ እንዲሆን ተደርጎ ተቀረጸ። የእነዚህ ድምር ውጤት አገሩን የማያውቅ፣ በኢትዮጵያዊ ማንነቱ የሚያፍር፣ ዐይቶት የማያውቀውን የውጭውን ዓለም የሚቀላውጥ መጢቃ ትውልድ ፈጠረ። ስለዚህ ዛሬ ላይ ሆነን ስናየው ጣሊያኖች በ1888 ዓም ዐድዋ ላይ ድል ሆነው ቢመለሱም፣ ከማይጨው ውጊያ በኋላ ግን የረዥም ጊዜ ዕቅዳቸውን እንዳሣኩ መገንዘብ ይቻላል።

ከፋሽስት ጣሊያን ወረራ በኋላ ዘመናዊ ትምህርት የቀመሰው ትውልድ፣ በወቅቱ እንደ ወረርሽኝ በመላው ዓለም በመሠራጨት ላይ የነበረው የኮሚኒስት ርዕዮተ-ዓለም ተከታይ ለመሆን ጣረ። «ያ ትውልድ» ለአገሩ ቀና ያሰበ መስሎት ጎትቶ ያመጣው ርዕዮተ-ዓለም ግን ከራሱ አልፎ የታላላቆቹን እና የታናናሾቹን ትውልዶች ቀርጥፈው የሚበሉ አምባገነን ሥርዓቶችን ፈጠረ። በዚህ ረገድ ወታደራዊው ደርግም ሆነ የትግሬ-ወያኔ ሥርዓቶች ምንጫቸው «የተማሪዎች እንቅስቃሴ» እየተባለ የሚጠራው ክስተት ነው ቢባል ማጋነን አይሆንም። በእርግጥ በአገራችን ላይ የደረሰውን እና አሁንም በመድረስ ላይ ያለውን መዓት ሁሉንም በዚያ ትውልድ የተሣሣተ የፖለቲካ አቅጣጫ ብቻ ማሳበብ ባይቻልም፣ ግዙፉን ድርሻ እንደሚወስድ ግን መጠራጠር አይገባም። ስለዚህ ዛሬ በኢትዮጵያዊነቱ የሚያፍር ትውልድ ቢፈጠር ሊደንቀን አይገባም፥ አባቱን አያውቅ፣ አያቱን ናፈቀ ተብሏልና።

ትውልድ በትውልድ ሲተካ በጎም ሆነ መጥፎ ነገሮች ይከሰታሉ። የአሁኑ ወጣት ትውልድ ያለፉት ትውልዶች ያከማቹት ጥሪት ውጤት ነው። ባንዳነት እንደ መሠልጠን እየተቆጠረ፣ በጥራዝ-ነጠቅነት ከውጪ «አዲስ መጣ» የተባለውን ርዕዮተ-ዓለም ስላነበነቡ ብቻ «አዋቂ» የሚያስብል ባህል እንዲስፋፋ እየተደረገ፣ ስለ አገር ታሪክ እና ስለ ሕዝብ ባህል ከማወቅ ይልቅ በምዕራቡ ዓለም የሚፈበረኩ ርካሽ የባህል ሸቀጦች ማራገፊያ መሆን የዘመናዊነት ምልክት ተደርጎ እየታየ፣ ዓለም በቴክኖሎጂ እየተመነደገ ሲሄድ የእኛ አገር ገዢዎች ሕዝብን በማስራብ እና በጅምላ በመፍጀት ከፍተኛ መዋዕለ-ንዋይ ሲያከማቹ እንድ ብልጠት እየተቆጠረ፣ ወዘተርፈ፤ ይህ አዲሱ ወጣት ትውልድ ከማን ያየውን እና የተማረውን የመልካም የዜግነት ምግባር እንዲያሣይ ይጠበቃል? ስለዚህ ከታሪክ ተወቃሽነት፣ ከትውልዱም ፈፅሞ መጥፋት እንድንድን በአንድነት ለትክክለኛው ኢትዮጵያዊ ማንነታችን ልዕልና እንነሣ!

ኢትዮጵያ በጀግኖች እና ቆራጥ ልጆቿ መስዋዕትነት ለዘለዓለም ፀንታ ትኖራለች!

The post «የእሣት ልጅ አመድ» የሆነው የዘመኑ ኢትዮጵያዊ ታሪካዊ ማንነቱን ያስከብር! – ሞረሽ ወገኔ የዐማራ ድርጅት appeared first on Zehabesha Amharic.

አልማዝ አያና በኳታር ዶሃ 3 ሺህ ሜትር ሩጫ አሸነፈች –ገለቴ ቡርቃም ድል ቀናት

0
0

485908858

(ዘ-ሐበሻ) ከደቂዎች በፊት በዳይመንድ ሊግ ውድድር በኳታሯ ዶሃ ከተማ በተደረገው ውድድር ኢትዮጵያዊቷ አልማዝ አያና በ3ሺ ሜትር የሴቶች ውድድር አንደኛ በመውጣት አሸነፈች::

አልማዝ ውድድሩን ለማሸነፍ የፈጀባት ጊዜ 8 ደቂቃ ከ23.1 ሰከንድ መሆኑ ታውቋል:: በዚሁ በዳይመንድ ሊግ ውድድር ኬንያዊቴ ሜርሲ ቸሮኖ 2ኛ ስትወጣ ውድድሩን በ8:26.36 ጨርሳለች:: በዚህ ውድድር 3ኛ የወጣችው ገለቴ ቡርቃ ስትሆን ውድድሩን በ8:28.49 ጨርሳለች::

ከ4ኛ እስከ 6ኛ ያለውን ቦታ የያዙት ኬንያውያኑ አትሌቶች ሲሆኑ እቴንሽ ዲሮ ነዳ 7ኛ ሆናለች:;

እንኳን ደስ አለን::

13112578_10154090036594373_1798588878_o

The post አልማዝ አያና በኳታር ዶሃ 3 ሺህ ሜትር ሩጫ አሸነፈች – ገለቴ ቡርቃም ድል ቀናት appeared first on Zehabesha Amharic.

አልማዝ አያና በኳታር ዶሃ 3 ሺህ ሜትር ሩጫ አሸነፈች –ገለቴ ቡርቃም ድል ቀናት

0
0

485908858

(ዘ-ሐበሻ) ከደቂዎች በፊት በዳይመንድ ሊግ ውድድር በኳታሯ ዶሃ ከተማ በተደረገው ውድድር ኢትዮጵያዊቷ አልማዝ አያና በ3ሺ ሜትር የሴቶች ውድድር አንደኛ በመውጣት አሸነፈች::

አልማዝ ውድድሩን ለማሸነፍ የፈጀባት ጊዜ 8 ደቂቃ ከ23.1 ሰከንድ መሆኑ ታውቋል:: በዚሁ በዳይመንድ ሊግ ውድድር ኬንያዊቴ ሜርሲ ቸሮኖ 2ኛ ስትወጣ ውድድሩን በ8:26.36 ጨርሳለች:: በዚህ ውድድር 3ኛ የወጣችው ገለቴ ቡርቃ ስትሆን ውድድሩን በ8:28.49 ጨርሳለች::

ከ4ኛ እስከ 6ኛ ያለውን ቦታ የያዙት ኬንያውያኑ አትሌቶች ሲሆኑ እቴንሽ ዲሮ ነዳ 7ኛ ሆናለች:;

እንኳን ደስ አለን::

13112578_10154090036594373_1798588878_o

The post አልማዝ አያና በኳታር ዶሃ 3 ሺህ ሜትር ሩጫ አሸነፈች – ገለቴ ቡርቃም ድል ቀናት appeared first on Zehabesha Amharic.

‎በደሴ‬ ከተማ ያሉ ነጋዴዎችና ባለሱቆች የስራ ማቆም አድማ አድርገው ነበር (የፍኖተ ዴሞክራሲ ራድዮ አጫጭር)

0
0
ሚያዚያ 27 ቀን 2008 ዓ.ም.ዜና (May 05, 2016 NEWS)
‪#‎በደሴ‬ ከተማ ያሉ ነጋዴዎችና ባለሱቆች የስራ ማቆም አድማ አደረጉ
‪#‎ከጋምቤላ‬ ተጠልፈው የተወሰዱ ከ100 በላይ የሚሆኑት ህጻናት ያሉበት ቦታ ታወቀ
‪#‎ከወያኔ‬ ጋር ግንኙነት ያላቸው ስደተኛ አስተላላፊዎች ተያዙ ተባለ
‪#‎የተመድ‬ የጸጥታው ምክር ቤት በደቡብ ሱዳን ወንጀል የፈጸሙ ለፍርድ እንዲቀርቡ ጠይቀ
‪#‎በኮንጎ‬ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ የአገሪቱ የፍርድ ሚኒስተር በተቃዋሚ ፓርቲዎች እጩ
‪#‎ተወዳዳሪ‬ በመሆኑ እንዲወዳደሩ በተወከሉት ግለስብ ላይ ክስ ሊመሰርት እንደሚችል ገለጸ
‪#‎በደቡብ‬ አፍሪካ ምክር ቤት ረብሻ ተፈጠረ
‪#‎ከስድስት‬ ቀን በኋላ በኬኒያ ከፈረሰው የመኖሪያ ህንጻ ውስጥ አንዲት ሴት በህይወት ተገኘች
 

ዝርዝር ዜናዎች
 በወሎ ደሴ የስራ ማቆም ያደረጉ ነጋዴዎችና ባለ ሱቆች ዛሬ ሶስተኛ ቀናቸው መሆኑ ታውቋል።
በደሴ ከተማ የሚገኙት ባለሱቆችና ነጋዴዎች የስራ ማቆም አድማ ለማድረገ የተገደዱት ከአቅም
በላይ የግብር ክፍያ የተጠየቁ በመሆናቸው የተነሳ ሲሆን ከሚያዚያ 24 እስከ ሚያዚያ 26 ድረስ
ባለሱቆችን ሁሉ ያሳተፈ የሥራ ማቆም አድማ መደረጉ ታውቋል። ነጋዴዎች ከአቅም በላይ የሆነ
የግብር ክፍያ መጠየቃቸውና ሁሉም ባለሱቅ የገንዝብ መሰብሰብና መመዝገቢያ እንዲያስገባ
በመጠየቃቸው ምክንያት ተቃውሟቸውን በሥራ ማቆም አድማ ከመግለጻቸውም በላይ
የተጣለባቸው የግብር ክፍያ ለመክፈል አቅም የሌላቸው ነጋዴዎች የንግድ ፈቃዳቸውን ለመመለስ
ቢያመለክቱም 20 ሺህ ብር እንዲከፍሉ መጠየቃቸው ተገልጿል። የወያኔ ባለሥልጣኖች የደሴ
ነጋዴዎች ላቀረቡት ጥያቄ አግባብ ያለው መልስ አለመስጠታቸው ሲታወቅ በዛሬው ዕለት
አንዳንዶቹ ወደ ስራ መመለሳቸው ታውቋል።

Dessie (ደሴ)

Dessie (ደሴ)

 ከትውልድ ቦታቸውና ከቀያቸው በግዳጅ ተጠልፈው የተወሰዱ ከ100 በላይ የሚሆኑ የጋምቤላ
ህጻናት ያሉበት ቦታ መገኘቱን የደቡብ ሱዳን ፕሬዚዳንት ቃል አቀባይ አስታውቋል። እንደ ቃል
አቀባዩቹ ከሆነ ከጋምቤላ ታግተው የተወሰዱት ህጻናት ከደቡብ ሱዳን ዋና ከተማ 300 ኪሎ ሜትር
ርቀት ሰሜናዊ ምስራቅ ግዛት ውስጥ እንዳሉ የታወቀ ሲሆን የአካባቢው ነገድ መሪዎችም ህጻናቱ
በቦታው ያሉ መሆናቸውን አረጋግጠዋል። ሰላሳ ሁለቱ ሕጻናት እንዴት እንደተፈቱና እንደተለቀቁ
የተሰጠ መረጃ የለም።

 የወያኔን ዘረኛና አምባገነን አገዛዝ በመጥላትና በኢትዮጵያ ያለውን አስከፊ ድህንነት በመሸሽ ወደ
አውሮፓ ወደ አረብ አገራትና ወደ ደቡብ አፍሪካ የሚደረገው ስደት ለአንዳንድ ግለሰቦችና ለወሮበላ
ቡድኖች በርካታ ገንዘብ የሚያስገኝ ስራ መሆኑ ሲታወቅ በዚህ ሰውን የማዘዋውር የወንጀል ስራ
ላይ ተሰማርተዋል የተባሉ ተጠርጣሪዎች በየአገሩ በቁጥጥር ስር እየዋሉ መሆናቸው ታውቋል።
በሚዴትራኒያን ባህር አቋርጠው በማልታ በኩል ወደ ጣሊያንና ሌሎች የአውሮፓ አገሮች
ኢትዮጵያውያንና የአፍሪካ ስደተኞችን በማሻገር ወንጀል ተከሶ የዋስ መብቱን ተጠቅሞ ተሰውሮ
የነበረው ሃዲሽ ኪዳኑ በቁጥጥር ስር መዋሉ ሲነገር በደቡብ አሜሪካ አገሮች በኩል ስደተኞች ወደ
አሜሪካ የሚያዘዋውሩ ወንጀለኞች እየተያዙና እየታደኑ መሆናቸውና ከተያዙት ውስጥ በኢትዮጵያ
ውስጥ ንብረትና የንግድ ሥራ ያላቸው እንዲሁም ከወያኔው ጋር ቀጥተኛ የነበራቸው መሆኑ
ታውቋል።

 የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የጸጥታው ምክር ቤት ረቡዕ ሚያዚያ 26 ቀን 2008 ዓ.ም. ባደረገው
ስብሰባ የተለያዩ ተጻራሪ ቡድኖችን ያካተተ የአንድነት መንግስት በደቡብ ሱዳን መመስረቱን አድንቆ
በግጭቱ ጊዜ ከፍተኛ ወንጀልና የሰብአዊ መብት ረገጣ ያካሄዱ ግለሰቦች ባስቸኳይ ለፍርድ
እንዲቀርቡ ጠይቋል ። ምክር ቤቱ የደቡብ ሱዳን የአንድነት መንግስት ተቋቁሞ ስራ መጀመሩ
በአገሪቱ ውስጥ ሰላምን ለማስፈን ትልቅና የመጀመሪያ እርምጃ መሆኑን ገልጾ በግጭቱ ወቅት የዓለም
አቀፍ ህጎችንና ደንቦችን በመተላለፍ የተደረጉትን የጭካኔ ርምጃዎችና የሰብአዊ መብት ረገጣዎች
ለፍርድ ለማቅረብ አስቸኳይ ርምጃዎች መወሰድ አለባቸው ብሏል። በሪክ ማቻርና በሳልቫ ኬር
መካከል ባለፈው ዓመት በተካሄደው ድርድር ከሁሉም የተወጣጣ አንድ ገለልተኛ የሆኑ የፍርድ
አካል ለማቋቋምና እንዲሁም አንድ የእርቅን የእውነት ፈላጊ ኮሚሽን ለመመስረት ስምምነት
የተደረገ መሆኑ የሚታወስ ሲሆን በትናንት የተመድ የጸጥታው ምክር ቤት ስብሰባ ላይ አሜሪካና
ሌሎች የምክር ቤቱ አባላት በአፍሪካ ህብረት የሚደገፍ የፍርድ አካል ባስቸኳይ እንዲቋቋም
ጠይቀዋል።

 በኮንጎ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ በሚቀጥለው ብሔራዊ ምርጫ የተቃዋሚ ፓርቲዎችን ወክለው
በእጩ ተወዳዳሪነት እንዲቀርቡ የተሰየሙት ሚስተር ካቱምቢ ኃላፊነቱን የሚቀበሉ መሆናቸውን
ተናግረዋል። ሚስትር ካቱምቢ በሰጡት መግለጫ ኃላፊነቱን በደስታና በክብር የሚቀበሉ መሆኑን
ገልጸው የተሰጣቸውን ኃላፊነት በድል ለማጠናቀቅ የሚቻለቸውን ሁሉ እንደሚያደርጉ ቃል
ገብተዋል። በሌላ በኩል በዚሁ ዕለት የአገሪ የፍርድ ሚኒስተር ሚስተር ካቱምቢ የውጭ አገር ዜግነት
ያላቸው ቅጥረኛ ወታደሮችን በጠባቂነት አሰማርተዋል የሚለውን ስሞታ እየመረመረ መሆኑን ገልጾ
ምርመራው ሲጠናቀቅ ክስ የሚመሰርት መሆኑን አስታውቋል። ሚስተር ካቱምቢ ለተሰነዘረባቸው
ክስ በሰጡት መልስ በመንግስት በኩል ሊቀርብ የተፈለገው የፈጠራና የውሸት ክስ እሳቸውን
ከውድድር ለማስቀረት የተደረገ ሴራ መሆኑን ገልጸው ኃላፊነታቸውን ለመወጣት እንቅፋት
እንደማይሆንባቸው ተናግረዋል። በሰላማዊ የስልጣን ሽግግርና በህግ የበላይነት የሚያምኑና
መሆናቸውን አስምረው የውጭ ዜግነት ያላቸው የግል ወታደሮች እንዳልቀጠሩ ገልጸዋል። ከአምስት
ዓመት በፊት በአገሪቱ የተካሄደው ብሔራዊ ምርጫ ነጻና ገለልተኛ ያልሆነ ማጭበርበርና ኃይል
በተቀላቀለበት ሁኔታ የተካሄደ ስለነበር የአሁኑ ፕሬዚዳንት የሚስተር ካቢላ አስተዳደር በከፍተኛ
ውጥረትና አለመረጋጋት ውስጥ አገሪቱን ሲመራ የቆየ መሆኑ ይታወቃል።

 በደቡብ አፍሪካ አንዲት ሴት የ19 ወር ህጻን ልጇን በኢንተርኔት አማካይነት በ340 የአሜሪካን ዶላር
ለመሸጥ ስትስማማ ተይዛ የአምስት ዓመት እስራት የተፈረደባት መሆኑ ታውቋል። የተወሰነባት
ቅጣት ለሶስት ዓመት ያህል በቤት ውስጥ ተገድባ ትምህርት እንድተወስድ የሚደረግ ሲሆን ሁለቱን
ዓመት ግን በእስር ቤት ታሳልፋለች ተብሏል። ሴትየዋ ልጇን ለመሸጥ የተገደድችው የህጻኑ አባት
ለልጁ ማሳደጊያ የሚከፍለውን ገንዘብ በማቋረጡና ችግር ላይ በመውደቋ ምክንያት መሆኑን
ገልጻለች። በደቡብ አፍሪካ የሰውን ልጅን በገንዘብ መሸጥ የእድሜ ልክ እስራት ወይም 6.7 ሚሊዮን
ዶላር መቀጫ የሚያስከፍል ሕግ ያለ ሲሆን የሕጻኑ እናት ቀለል ያለ ቅጣት እንዲሰጣት የተደረገው
ልጁን ለመሸጥ ያደረገችው ሙከራ የገንዘብ ትርፍ ለማግኘት ሳይሆን ከችግር መሆኑ ስለታመነበት
ነው ተበርካታ ገንዘብ ለማግኘት ባለመሆኑ ነው ተብሏል።

 ትናንት ረቡዕ ሚያዚያ 26 ቀን 2008 ዓ.ም. በደቡብ አፍሪካ የአገሪቱ ፕሬዚዳንት ሚስተር ዙማ ስለ
በጀት ጉዳይ ለምክር ቤቱ አባላት ንግግር ለማድረግ በሚዘጋጁበት የኢኮኖሚ ነጻነት ታጋዮች ፓርቲ
የሚባለውን የተቃዋሚ ፓርቲ የሚወክሉ 10 የምክር ቤቱ አባላት ፕሬዚዳንቱ መናገር የለባቸውም
የሚል ድምጽ በማሰማት እንዳይናገሩ እክል በመፍጠራቸው የጸጥታ ኃይሎች ሰዎችን ከምክር ቤቱ
መሰብሰባያ አዳራሽ ለማስወጣት ሙከራ ባደረጉበት ወቅት ቦክስ እና እርግጫ የተቀላቀለበት ድብደባ
ተካሄዶ እንደነበር ታውቋል። ተቃዋሚዎቹ ከምክር ቤቱ እንዲወጡ ከተደረገ በኋላ ፕሬዚዳንቱ
ያቀደቱን ንግግር ለማደረግ ችለዋል። ቀደም ብሎ የደቡብ አፍሪካ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ሚስተር ዙማ
የአገሪቱን ሀብት ያለአግባብ ተጠቅመዋል ብሎ የፈረደ መሆኑ ይታወቃል። አንድ ሌላ ፍርድ ቤት
4
ደግሞ በሚስተር ዙማ ላይ ቀርበውና በኋላ ተሽረው የነበሩ ከ800 በላይ የሚሆኑ ክሶች እንደገና
እንዲታዩ በመወሰኑ ዙማ በሚመሩት የደቡብ አፍሪካ አስተዳደር ላይ ከፍተኛ ውጥረትና ጫና
የፈጠረ መሆኑ ይታወሳል።

 በኬኒያ ባለፈው ሳምንት አንድ የመኖሪያ ህንጻ ከተረደመሰ ከስድስት ቀን በኋላ በተደረገው ፍለጋ
አንዲት ሴት በህይወት ልትገኝ የቻለች መሆኗን የኬኒያ መንግስት ባለስልጣኖች ሐሙስ ሚያዚያ 27
ቀን 2008 በሰጡት መግለጫ ገልጸዋል። መናገር የምትችለውና በጥሩ መንፈስ ላይ ትገኛለች
የተባለችው ይችው ሴት ከህንጻው ፍርሽራሾች ገና ያልወጣች ስትሆን በአካብቢው የሚገኙ የሕክምና
ባለሙያዎች ግሎኮስና ኦክሲጅን እየሰጧት መሆኑ ታውቋል። በትናንትናው ዕለትም አንዲት
የስድስት ወር ህጻን ከእነህይወቷ መትረፏ የተነገረ ሲሆን ዘግይቶ እናትየዋ ሞቷ መገኘቷ ተነግሯል።
የህንጻው መደርመስ ስድሰተኛ ቀኑን ያስቆጠረ ሲሆን እስካሁን 36 ሰዎች መሞታቸውና የ70 ሰዎች
ሁኔታ ምን እንደሆኑ አለመታወቁ ተገልጿል።

ዝርዝር ዜናዎች
 የወያኔ አገዛዝ ስልጣን ከያዘበት ጊዜ ጀምሮ እንደ አሸን የፈሉትን ቡና ቤቶችንና የጭፈራ ቤቶችን
ምዝገባና ቆጠራ ሊያካሂድ መሆኑ ታውቋል። ከዚህ በተጨማሪ የአስጎብኝ ድርጅቶች እየተባሉ
የተከፈቱት የንግድ ድርጅቶች ምዝገባና ቆጠራ ይካሄድባቸዋል። ቆጠራውና ምዝገባው ለምን እንዳስፈለገ
ወያኔ የገለጸው ነገር ባይኖርም ምናልባት የአገልግሎት ክፍያ ጭማሪ ሊያደርግባቸው በማሰብ ሊሆን
እንደሚችል ተገምቷል። ምዝገባውና ቆጠራው ከግንቦት 1 ቀን እስከ ግንቦት 20 ቀን 2008 ዓ.ም ድረስ
በአዲስ አበባ የሚካሄድ ሲሆን በሌሎች ከተሞች ቀጣይነት ይኑረው አይኑረው የታወቀ ነገር የለም።
የወያኔ መሪዎችና ባለስልጣኖች ሌላ ዜጋ የማይገባበት የራሳቸው መስከሪያ ቡና ቤቶችና መዝናኛ
ሆቴሎች እንዳላቸው ይታወቃል።

 ሰላሳ የሚሆኑ ኢትዮጵያውያን ሴቶች ከዱባይ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ጣቢያ ወደ አዲስ አበባ
እንዲመለሱ መገደዳቸው ታወቀ። ኢትዮጵያውያን ሴቶቹ ቲኬት ገዝተው በፋላይ ዱባይ አየር መንገድ
ተሳፍረው ዱባይ ይግቡ እንጅ ዱባይ እንደደረሱ ትክክለኛ የመጎብኚያ ቪዛ የላችሁም ተብለው
በአውሮፕላን ጣቢያው እንደሚገኙ ታውቋል። የፋላይ ዱባይ አየር መንገድ ቃል አቀባይ የተወሰኑ
የኢትዮጵያ መንገደኞች ቡድን ወደ አዲስ አበባ እንዲመለሱ እንደሚደረግ ማረጋገጫ ሰጥተዋል። ይሁን
እንጅ ትክክለኛ ቪዛና የመጎብኚያ ፈቃድ የሌላቸው ሴቶች እንዴት ከሀገር ወጡ የሚለው ጥያቄ አነጋጋሪ
ሆኗል።

 የኢትዮጵያው ድርቅና ረሃብ አየከፋ መምጣቱና በተለይም በሕጻናት ላይ አስጊ ሁኔታን እየፈጠረ መሆኑን
የዕርዳታ ድርጅቶች አስታውቀዋል። ስድስት ሚሊዮን ኢትዮጵያውያን ህጻናት በዚህ የድርቅና የረሀብ
ሰለባ እንዳይሆኑ ጥሪ ያቀረበ ሲሆን ድርቁና ረሃብ ከአሳሳቢነት ወደ አስጊነት መሸጋገሩ በተለይም
ለሕጻናት መድረሻው ጊዜ አሁን ነው ብሏል።

 የወያኔ አገዛዝ ፖለቲካውን የጦር ኃይሉን የፖሊስና የደህንነት መስሪያ ቤቱን በትግራይ ተወላጆች ብቻ
ካደራጀ ወዲህ በንግድ ዓለምም በሙስናዋ እመቤት በአዜብ መስፍን የሚመራ የነጋዴ ቡድን በተለይ
የቡና ንግዱን ሙሉ በሙሉ መቆጣጠራቸውና ቡና ላኪነት በትግራይ ተወላጆች እጅ እንዲወድቅ
መደረጉ ይታወሳል። ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በቡና ላኪነት የተመዘገቡ ቡና መላክ የጀመሩ ላኪዎች ከ 19
ሺ ሜትሪክ ቶን በላይ ቡና ደብቃችኋል በመባል ከንግዱ ዓለም እንዲታገዱ መደረጉ ታውቋል።
እንዲታገዱ የተደረጉት የቡና ላኪዎች 54 እንደሆኑና ደበቁት የተባለውም ቡና 7.6 ሚሊዮን ዶላር
የሚያወጣ ነው ተብሏል። ቡና ለወያኔ ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ ማስገኛ የነበረ ሲሆን የወያኔ ነጋዴዎችና
መሪዎች በሚሰሩት አሻጥርና ገንዘብ የማሸሽ ሚስጥር የአበባ ሽያጭ የቡና ገቢውን እየተካ መምጣቱ
ይታወሳል።

 የደቡብ ሱዳን ታጣቂዎች በጋምቤላ ወረራ በመፈጸም ከ200 በላይ ገድለው ከመቶ በላይ አፍነው ንብረት
አውድመው ከጠፉ ከሁለት ሳምንታት በኋላ የወያኔ ወታደሮች በደቡብ ሱዳን እንቅስቃሴ መጀመራቸው
ታውቋል። የአይን ምስክሮች ለሱዳን ትሪቡን ጋዜጣ እንደገለጹት ብዛት ያላቸውና በ 20 ታንኮች የታጀቡ
የወያኔ ወታደሮች በፓቼላ በኩል ወደ ደቡ ሱዳን እየገቡ መሆናቸውንና የጦር አውሮፕላኖችም የቅኝት
በረራ እያደረጉ መሆናቸውን ገልጸዋል። የደቡብ ሱዳን ባለስልጣኖች የወያኔን ወታደራዊ እንቅስቃሴ
መስማታቸውን ገልጸው ዝርዝር መርጃ ግን የለንም ብለዋል።

 የሱማሊያ አማጺ ኃይልና ከአልቃይዳ ጋር ንኪኪ ያለው አልሸባብ ማክሰኞ ዕለት በሞቃዲሾ አውሮፕላን
ጣቢያ ባለው የአፍሪካ ኅብረት ሰላም አስከባሪ ኃይል የጦር ሠፈር ላይ የሞርታር ጥቃት ማድረሱን
አምኗል። አልሸባብ ሞቃድሾ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ጣቢያ ውስጥ ባለው የጦር ሰፈር ላይ ድብደባ
ማካሄዱንና በሰው ህይወትና በንብረት ላይ ጉዳት ማድረሱን በደፈናው ይግለጽ እንጅ ስለደረሰው ጉዳት
ዝርዝር መግለጫ አልሰጠም። በሶማሊያ የተመድ የሰላም አስከባሪ ኃይል ቃል አቀባይ በበኩላቸው
የአልሸባብ የሞርታር ጥይቶች ከጦር ሰፈራቸው ውጭ ማረፋቸውን በመግለጽ በሰውና በንብረት ላይ
የደረሰ ምንም ዓይነት ጉዳት አለመድረሱን ተናግረዋል። ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የአልሸባብ መሪዎችና
ኮማንደሮች በአሜሪካ ድሮን በመገደላቸው ብቻ አልሸባብ ተዳክሟል የሚል አስተያየት ይሰጥ እንጅ
የአልሸባብ ጥቃት መቀጠሉ የድርጅቱን ጥንካሬና የሶማሊያ የሰላም ጊዜ ገና ሩቅ መሆኑን ያሳያል
ተብሏል።

 በላቦራቶሪ ውስጥ የተሰራ አንትራክስ የሚባልን ተላላፊ በሽታ በማሳራጨት የሽብር ተግብር ላይ
ለመሰማራት ያቀደውንና ከአልካይዳ ጋር ግንኙነት አለው ተብሎ የሚንጠረጠረውን መሀምድ አብዲ
አሊ የተባለውን ግለሰብ ከሚስቱ እና ከሌላ አንዲት ሴት ጋር በቁጥጥር ስር ያደረገ መሆኑን የኬኒያ
ፖሊስ ገልጿል። ሽብሩን ለማካሄድ በእቅዱ ላይ ተባባሪ የነበሩ ሌሎች ሁለት ሰዎች አምልጠው
እየተፈለጉ መሆናቸውም ተገልጿል። በኬኒያ ሆስፒታል የነጻ ህክምና አገልግሎት ይሰጥ የነበረው
መሀመድ አብዲ አሊ ኬኒያውያንን በመቀስቀስ ለሽብር ተግባር ሲያዘጋጅ የቆየ ነበር የተባለ ሲሆን
የህክምና ባለሙያዎችን በማሳተፍ በላቦራቶሪ የተሰራ የአንትራክስ በሽታ ለማሰራጨት እቅድ
እንደነበረው ተደርሶበታል። ሚስቱና የቅርብ ተባባሪ የነበረችው ተማሪዋ ኑሰይባ መሀመድ ሃጂ
የተባለችውና ጓደኛዋ ፋጡማ መሀመድ ከሚኖሩበት ከኡጋንዳ የተያዙ መሆናቸውም ተነግሯል።
የመሀመድ አብዲ ሌሎች ተባባሪዎች አምልጠው የተደበቁ ሲሆን ሰዎቹን ይዞ ላመጣ ወይም ያሉበትን
ለጠቆመ የኬኒያ መንግስት 20 ሺ የአሜሪካ ዶላር ለመክፈል ዝግጁ እንደሆነ ገልጿል። ቡድኑ በሊቢያ
በሶሪያ ካሉ የአልካይዳ ቡድኖች ጋር ግንኙነት እንዳለው ተደርሶበታል።
በተያያዘ ዜና ባለፈው ሳምንት አርብ ሚያዚያ 21 ቀን ከፈረሰው አንድ ህንጻ ውስጥ በህይወት ያሉ ሰዎችን
ለማውጣት ፍለጋው የቀጠለ ሲሆን ማክሰኞ ሚያዚያ 25 ቀን 2008 ዓም አንዲት የስድስት ወር ህጻን
በህይወት የተገኘች መሆኑ ታውቋል። በህንጻው መደርመስ 23 ሰዎች መሞታቸውና በርካታዎች
መቁሰላቸው ሲነገር ከ93 በላይ የሚሆኑ ሰዎች መዳንና አለመዳናቸው አልታወቀም ተብሏል። ከአራት
ቀን በኋላ የስድስት ወር ሕጻን በህይወት መገኘቷ ሌሎች በህይወት ሊኖሩ ይችሉ ይሆናል የሚለውን
ተስፋ ከፍ አድርጎታል። ሕጻኗ ከፈሳሽ እጥረት በስተቀር ምንም ጉዳት ያልደረሰባት መሆኑ የታወቀ ሲሆን
አብራት የነበረችው እናቷ በህይወት ትኑር አትኑር እስካሁን አልታወቀም። በሌላ ቦታ ስራ ስለነበር
ከአደጋው ያመለጠው አባቷ የልጁን በህይወት መገኘት ከፍተኛ ተአምር ነው ብሎታል።

 በምስራቅ ኮንጎ ሶስት የቀይ መስቀል ሰራተኞች ተጠልፈው የተወሰዱ መሆናቸውን አንድ መንግስታዊ
ያልሆነ ድርጅት ማክሰኞ ሚያዚያ 25 ቀን ገለጸ። ሶስቱም ሰዎች ሾፌሮች ሲሆኑ ጎማ ከተባለችው
የምስራቅ ኮንጎ ከተማ ክብሪዚ ወደ ተባለች አንድ ሌላ ከተማ እቃ የያዙ መኪኖችን እያሽከረከሩ
በነበሩበት ወቅት ነው። ጠላፊዎቹ የታጠቁ ሚሊሺያዎች መሆናቸው የአካባቢው ሰዎች የተናገሩ ሲሆን
መኪናዎቻቸውን መንገድ ላይ ትተው እነሱን ወደ ጫካ ይዘዋቸው እንደገቡ ገልጸዋል። ማዕከሉ ጄኒቫ
የሆነው የዓለም አቀፉ የቀይ መስቀል ተቋም ዳይሬክተር ዶሚኒክ ስቲል ሃርት ማክሰኞ ዕለት በሰጡት
8
መግለጫ ድርጅቱ ሰዎቹን ለማስፈታት የተቻለውን ሁሉ ያደርጋል ብለዋል። በምስራቅ ኮንጎ የመንግስቱ
ተቃዋሚ የሆኑ የተለያዩ የታጠቁ ቡድኖች የሚንቀሳቀሱ መሆናቸው ይታወቃል።

በተያያዘ ዜና በዚሁ በምስራቅ ኮንጎ ማንነታቸው ያልታወቀ ሰዎች ማክሰኞ ሚያዚያ 25 ቀን 2008 ዓም
ከምሽቱ 2 ሰዓት እስከ 4 ሰዓት ባለው ጊዜ ውስጥ አንድ መንደር ላይ ወረራ አካሂደው በቆንጨራና
በመጥረቢያ 16 ሰዎች የገደሉ መሆናቸውን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰላም አስከባሪ ኃይል እና
የኮንጎ መንግስት ባለስልጣኖች ገልጸዋል። ባለስልጣኖቹ ዛሬ ረቡዕ ሚያዚያ 26 ቀን በሰጡት መግለጫ
አሸባሪዎቹ ለጥበቃ ከተሰማራው ኃይል ተሰውረው ወደ መንደሩ የመጡ መሆናቸው ጠቅሰው ሰዎቹ
አላይድ ዴሞክራቲ ፎርስ (ADF)የተባለው የዩጋንዳ አማጺ ቡድን አባላት መሆንና አለመሆናቸው
አልታወቀም ብለዋል፡፤ አላይድ ዴሞክራቲክ ፎርስ የተባለው ድርጅት ተደጋጋሚ የሽብር ተግባሮችን
የፈጸመ ሲሆን በፈረጆቹ አመት 2014 ብቻ በአካባቢው ከ500 የሚበልጡ ሰዎችን መግደላቸው
ተዘግቧል።

 ናይጄሪያ ከሌጎስ ግዛት ነዳጅ ማውጣት የጀመረች መሆኑ ተነገረ። ከ25 ዓመት የፍለጋ፣ የጥናትና
የግምባታ ሥራ በኋላ ማውጣት የተጀመረው የነዳጅ ክምችት በቀን 40 ሺ በርሜል የማውጣትና ከ
750 ሺ በርሜል በላይ የማከማቸት አቅም እንዳለው ተገልጿል። እስካሁን ናይጄሪያ ነዳጅ ስታወጣ
የነበረው ከደቡብ ዴልታ ግዛት ሲሆን ከነዳጁ ገቢ ተመጣጣኝ ገንዝብ አለተሰጠንም በማለት የተለያዩ
ቡድኖች የአመጽ እንቅስቃሴዎች ሲካሄዱ መቆየታቸው የሚታወቅ ነው። የነዳጅ ሽያጭ የናይጄሪያ
መንግስትን በጀት በከፍተኛ ደረጃ እየሸፈነ ቢሆንም በቅርቡ በነዳጅ ላይ የነበረው የዋጋ ማሽቆልቆል
የበጀቱን መጠን ዝቅተኛ አድርጎት እንደነበር ይታወቃል።

The post ‎በደሴ‬ ከተማ ያሉ ነጋዴዎችና ባለሱቆች የስራ ማቆም አድማ አድርገው ነበር (የፍኖተ ዴሞክራሲ ራድዮ አጫጭር) appeared first on Zehabesha Amharic.

አርቲስት ጀምበር አሰፋ በመልካም ሁኔታ ላይ እንደምትገኝ ታወቀ

0
0

13124810_10206571240062134_4666535284324570389_n
(ዘ-ሐበሻ) ተወዳጇ ተዋናይት ጀምበር አሰፈ በሚኒሶታ የተሳካ ቀዶ ጥገና አድርጋ ጤንነቷ በመልካም ሁኔታ ላይ እንደሚገኝ ለዘ-ሐበሻ የደረሰው መረጃ አመለከተ:: ከኩላሊት ህመም ጋር በተያያዘ ቀዶ ጥገና እንዳደረገች የተሰማው አርቲስቷ የህክምና ወጪዎቿን በሃገር ቤት እና በሚኒሶታ ያሉ ኢትዮጵያውያን አርቲስቶች እንደቻሉ ለማወቅ ተችሏል::

አርቲስቷ በሚኒሶታ እንደገመገኘቷ በሚኒሶታ የሚገኙ አድናቂዎቿ ሄደው እንዲጠይቋት በማሰብ ዘ-ሐበሻ የሚቀርቧት አርቲስቶችን ስለምትገኝበትና ስለተኛችበት ሆስፒታል መረጃ ብትጠይቅም ምላሽ ልታገኝ አልቻለችም::

አርቲስት ተስፋዬ ማሞ በፌሰቡክ ገጹ ስለ አርቲስት ጀምበር አሰፋ ባሰፈረው መረጃ: “ወዳጆቻችንና ጓደኞቻችን ሁሉ እህታችን ጀንበር አሰፋ መታመሟን በሰማችሁ ጊዜ በአስፈለጊው ነገር ሁሉ ከጎኗ ለመቆምና የሚቻላችሁን ለማድረግ ያሳያችሁት የደግነት ስሜት ሁሉ የሚረሳ አይደለም፡፡ ከህመሟ ፈጥና እንድትፈወስ ለማድረግ አዳነች ወ/ገብርዔል፣ ቴዎድሮስ ተ/አረጋይ፣ ተፈራ ወርቁ ቅድስት ገብረሥላሴ የውብዳር አንበሴና እኔ ኮሚቴ አቋቁመን መንቀሳቀስ በጀመርንበት ወቅት ብዙ ሳንለፋ ሳንወጣና ሳንወርድ ሰለሞን ቦጋለ፣ ሳምሶን ታደሰ (ቤቢ) እና ሌሎች ጓደኞቻቸው ለችግሩ ቀድመው በመድረስ ያሳዩት ወገናዊነት እጅግ አስደሳችና ፈፅሞ የሚረሳ አልነበረም፡፡ በዚህም ኢትዮጵያውያን የኪነጥበብ ሰዎች ራሳቸው ለራሳቸው መድረስ እንደሚችሉ ለመጀመሪያ ጊዜ የታየበትን ልገሳ በማድረግ 450 ሺ ብር ያህል ወጭ አድርገው ውጭ ሀገር ሄዳ እንድትታከም ቅድሚያውን በመውሰዳቸው ምስጋናችን እጅግ ከፍ ያለ ነው፡፡” ካለ በኋላ “አሜሪካን ሃገር ስትሄድም በቅድሚያ የተቀበሏትና ሁኔታዎችን ሁሉ ያመቻቹላት አቶ መላኩና ባለቤቱ፣ ሁሌም ከጎኗ ሳትለይ እንዳይከፋት የታተሩት ጓደኛችን እመቤት ወልዴ (አዳል) እና ቤተሰቧ እንዲሁም በአሜሪካን ሀገር ሚኒያፖሊስ እና አካባቢው የሚኖሩ እነራሄል፣ አስቴር፣ ዮሃንስ፣ ሃይማኖት እና ሌሎችም የጥበብ ቤተሰቦች ሁሉ ያሳዩት በጎነትና ያደረጉት ርብርብ እጅግ ከባድና አስቸጋሪ የነበረው የጀንበር ህክምና የተሳካ እንዲሆን ስላደረጉ በያሉበት ከፍ ያለ ምስጋናችን ይድረሳቸው ውለታቸውንም ቸሩ አምለክ ይክፈላቸው፡፡ በያላችሁበት ሆናችሁ በፀሎትና በመልካም ምኞት ከጀንበር ጎን ለነበራችሁ ሁሉም ምስጋና ይግባችሁ፡፡ ጀምበር ከህመሟ ሙሉ በሙሉ ተፈውሳና አገግማ ወደ ሥራዋና ቤተሰቧ በሙሉ ጤንነት ትመለስ ዘንድም የሁላችን መልካም ምኞት ነው፡፡” ብሏል::

ዘ-ሐበሻ በሚኒሶታ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን አርቲስቷን እንዲጠይቁ የተኛችበትን ሃኪም ቤት መረጃ አሰባስባ ለማቅረብ አሁንም ትሞክራለች::

The post አርቲስት ጀምበር አሰፋ በመልካም ሁኔታ ላይ እንደምትገኝ ታወቀ appeared first on Zehabesha Amharic.

ዮናታን ተስፋዬ የአገዛዙ ውጤት ነው! – (ከፕ/ር መስፍን ወ/ማርያም)

0
0

Yonatan Regas - Satenaw
አገዛዝ ሰው እንደሚያጠፋው ሁሉ፤ ሰውንም ይፈጥራል፡፡ ያልተወሰኑ ሰዎችን በተወሰኑ መልኩ ይቀይራል፡፡ የሕይወት መስመርንም በሠፊው ይቀይሰዋል፡፡
ከአንድ የግል ትምህርት ቤት የእንግሊዝኛ አስተማሪነት ወደ አገራዊ ጉዳይ ዘበኝነት የተቀላቀለው ወጣት ዮናታን፤ በዚሕ እድሜው ዘመኑን ሆነ የአገዛዝ ፈቃድ ባልወሰነው መልኩ ፤ ጀብዱን ፈጽሟል፡፡ የአገዛዝን አስከፊነት /መልከ ጥፉነት/ በወኔው መንዝሯል፡፡ ታግሏል፡፡ ለብዙዎችም አርኣያ ሆኗል፡፡

የአገዛዝ ሥርዓቱ ተስፋ ካስቆረጣቸው እና ሰላማዊ ትግል የሚያስከፍለውን መስዋዕትነት መቀበል ካዳገታቸው ግለሰቦች ውስጥ ሊመደብ ይችላል ፡፡ ወጣት ዮናታን፡፡
እዚህ ላይ የምናቀርበው ጉልበተኛውን ከሳሽ፣ ራሱ ዳኛ፣ ራሱ ፈራጅ የሆነውን የአራዊቶች ስብስብ ሳይሆን፤ ግለሰቡ ከምን ተነስቶ ወደ ምን እንደተጓዘ (እንደተቃኘ) ምን ምን ምክንያቶች ወደዚህ ጎዳና እንደመሩት.. ወዘተ ላይ ብናተኩር ይበጀናል፡፡ (የወደቀ ዛፍ ምሳር ይበዛበታል ሲባል እንሰማለን)

በኣንዳንድ የግድግዳ ላይ ጽሑፎቹ ማስቀመጥ እንደጀመረው፤ የዘውግ ፖለቲካ ላይ ርዕስ ፈጥሮ የሚሰማውን እና የሚታየውን መጻፉ ኣንዳንዶቹን ማስደመሙ ኣልቀረም፡፡ “የጎንደርኛ ሙዚቃ ሲጫወት ኣንደኛው ልቡ ሲሞቅ ሌላኛው የኦሮምኛውን ሲቀኝ እንደ ብሔርተኛ ይታያል” አይነት መልዕክት ያዘለ ሐሳቡ እውነትም አገዛዙ ባሳደረው የብሔርተኛ ፖለቲካ ጫና የተሰለቡ ግለሰቦች መብዛታቸውን ያሳየናል፡፡ በዚህ ሐሳብ ላይ ዮናታን ያነሳው ነጥብ መሬት ላይ የማይወድቅ ሕጸጽ የሌለበት ሐሳብ ነው፡፡ “ኢትዮጵያ” “ኢትዮጵያ” “አንድነት” “አንድነት” የምንል ሰዎች የልዩነት ሰበዞችን መቀበል እና መረዳት ይኖርብናል፡፡ ዮናታን ይሕ አገላለጹ ከወዳጆቹ ጋር አላትሞታል፡፡ ወዳጆቹ እንዳልነበሩ ወዳጆቹን በጥቅስ ውስጥ ማስገባት በተሻለ ይገልጽልናል፡፡

“ወዳጆቹ” ስሙን ወደ ቴሬሳ መቀየሩንም እንደ ጉድለት ቆጥረውበት፤ ሌላ ስም ለጥፈውበት፤ ድምጻቸውን ሲየስተጋቡ አይተናል፡፡ ኢትዮጵያዊ ፓርቲ ውስጥ ተቀላቅሎ መታገልን ሲመርጥ ልዩነቶችን የሚያስተናግድ ማሕበረሰብ አለ፤ አልጋውን አንጥፎ ወንበሩን አሰናድቶ ይጠብቀኛል ያለው ማሕበረሰብ፤ “ይሕችን ልዩነት” አጎላሕብኝ /በሚል ሰበብ ይመስላል/፤ አልጋው ላይ እሾሕ እንደተከለበት ሲያስተውል ክፉኛ ማዘኑን የምንረዳው እንረዳዋለን፡፡

በዚህ አጸፋ ውስጥ ሆኖ ከ“ወዳጆቹም” ከጠላቶቹም የተላተመው ወጣቱ፤ ኣገዛዙ ያሳደረውን የሥልጣን ሱስ በምን መልኩ ሊመልሰው እንደሚችል ምርጫውን ለመምረጥ አዳጋች ጊዜ ላይ ወድቋል፡፡ ወዳጆቹ ያልተረዱለትን የልዩነት መስመር “በኦሮሞ ፕሮቴስት” መፈክር ውስጥ ጩኸቱን ሲያሰማው ተገኘ፡፡ የነጃዋርን ድምጽ እንደ ገደል ማሚቶ ማስተጋባት ተያያዙበት፡፡ ትግሉ የብሔር እና የተወሰነ ማሕበረሰብ ትግል ሆኖ እንዲታይ ማስቻል ቀላል የሚባል ተጽእኖ አይደለም፡፡ የዘውጌ ፖለቲካን ክፉ ከሚያደርገው መስመር አንዱም ይሕ ነው፤ የአንድነትን ኃይል ከማርበትበቱም አልፎ የሚቀድመውን ማስከተል፤ የሚከተለውን ማስቀደም እንደ መርህ መታዬት ይጀምራል፡፡ ፈረሱ መቅደም ሲገባው ጋሪው እንደሚባለው፡፡ ኦሮሞ ፕሮተስት ኢትዮጵያ ፕሮቴስት ተብሎ ቢሰናዳ ይሕ አገዛዝ አንድ ቀን ኣያድርም፡፡
የአመጽ መንገዶችን ማስተጋባት የጀመረው ከውስጡ በተተበተበው የአገዛዙ ክፉ እጣ ፈንታ አማካኝነት ነበር፡፡ እጣ ፈንታን የመወሰን እና የመከላከል እንዲሁም የመምረጥ “ፋንታው” እኛ ጋር ነው፡፡ ቢያንስ በእጣ ውስጥ ፋንታ እንዳለ የምንገነዘበው ጥቂቶች እንሆናለን፡፡

ዮናታን ነጻነትን ከሚሰልቡ እጆች ተላቅቆ፤ የአገዛዙን ጭቆናና በደል ተረድቶ በሁሉን አቀፍ ኢትዮጵያዊ ጉልሕ ተቃውሞ፤ እልህ አስጨራሹን እና መስዋዕት አስከፋዩን ሰላማዊ/ሰማያዊ ትግል እንደሚቀላቀል ተስፋ እናደርጋል፡፡ በዮናታን ውስጥ ፈረሱን ከጋሪው ማስቀደም የሚከብድ ኣይደለምና!!
እግዜር ያጽናው!! ከመላው ቤተሰቡ እና ወዳጆቹ ጋር፡፡

The post ዮናታን ተስፋዬ የአገዛዙ ውጤት ነው! – (ከፕ/ር መስፍን ወ/ማርያም) appeared first on Zehabesha Amharic.

ከጃን ሸላሚነት ወደ ጃንሆይነት!(በ.ሥ)

0
0

እንኳን ለሠራተኞች ቀን በሰላም አደራሳችሁ፡፡ ያው በኔና በብጤዎቼ አቆጣጠር እያንዳንዱ ቀን ያለም ሠራተኞች ቀን ነው፡፡
ባገራችን ሁለት አይነት መደቦች ነበሩ፡፡ ለፍቶ አዳሪና ቀማኛ፡፡ ከንግሥተ ሳባ እስከ ዛሬ ያለው ያገራችን ታሪክ ባመዛኙ መንግሥታዊ ሌብነት ነው ማለት ይቻላል፡፡ ሥልጣንን ተገን እስካደረገ ድረስ ዝርፍያ ነውር አይደለም፡፡ ዘራፊዎችን ታሪክ በደማቅ ይዘክራቸዋል፡፡ ታቦተ ጽዮንን ሠርቆ ካመጣው ቀዳማዊ ምኒልክ ጀምሮ ለህዝብ ጥቅም ሲባል የህዝብ ባንክ እስከተዘረፈበት ” አክሱም ኦፕሬሽን“ ድረስ ስርቆት የጀብድ ምልክት ሆኗል፡፡
ገበሬዎችና ለፍቶ አዳሪዎች መታሰቢያ የላቸውም፡፡ የገበሬ ሃውልት አይተህ ታውቃለህ ወዳጄ? “ ደማችንን አፍሰስን ” የሚል እንጅ “ላባችንን አፍስሰን” ብሎ የሚኮራ ዘመናይ ገጥሞህ ያውቃል? ኧረ ለመሆኑ፤ አዝማሪ የሚዘፍንለት የታወቀ አንጥረኛ ሰምተሽ ታውቂያለሽ?
“ከፈረሰኞች የምናውቃቸው
በሻህ አቦየ ኃይሌ አንዳርጋቸው ”
ተብሎ ይዘፈን ነበር፡፡ ለፈረሰኞች ኮርቻ ግላስና ልጓም የሚሠሩ ሰዎች ግን እንደበሻህ አቦየና እንደ ኃይሌ አንዳርጋቸው አይታወቁም፡
ለፍቶ አዳሪ ስም የለውም፤ታሪክ የለውም፡፡
እንዲያ ነው!!
አንዳንዴ ለፍቶ አዳሪዎች ንቀትና ድህነት ሲያንገፈግፋቸው ይሸፍቱ ነበር ፡፡ ባፍሪካችን ብቸኛ የክብርና የጥቅም ምንጭ የሆነውን የመንግሥት ስልጣን ለመቆጣጠር ሞክረዋል ፡፡ ከነዚህ ሞካሪዎች አንዱ በኢያሱ ቀዳማዊ ዘመን ተነሥቶ ወድቋል፡፡
የኢያሱ ታሪክ ጸሐፊ ይህንን ሽፍታ በጣም ስለናቀው ስሙን እንኳ መዝግቦ ሌያስተላልፍልን አልፈቀደም ፡፡ ሁሉም ሽፍቶች በሚጠሩበት የወል ስም “ ወረኛ ” ብሎት አልፏል ፡፡ እኔ በሙያ ስሙ አክብሬ፤ “ጃን ሸላሚ” እለዋለሁ፡፡ ጃን ሸላሚ ማለት ንጉሥ የሚጠቀምባቸውን ጌጦችና ቁሳቁስ የሚሠራ ማለት ነው፡፡ ያለ ጃን ሸላሚ ንጉሥ መናኛ፤ ቀትረቀላል ሰው ነው፡፡

Beweketu Seyoun joke about African leaders summit [Very Funny]
ያ ጃን ሸላሚ ከተወለደበት አገር ወጥቶ፤ ወደማያቁት አገር ከተሻገረ በኋላ ራሱን የንጉሥ ልጅነኝ ብሎ አስተዋወቀ፡፡ የተወሰነ ተከታይ አፍርቶም ነጋሪት እያስመታ አንድ ሐሙስ ከነገሠ በኋላ በጦርነት ተማረከ ፡፡ አደባባይ ላይ ለፍርድ ቀርቦም በመኳንንት ተመረመረ፡፡
መርማሪ- ነገድህ ከየት ነው?
ጃንሸላሚ: -ከባለጌ ነገድ ነኝ፡፡ ( የዛሬውን አያርገውና ባለጌ ማለት ባላገር ማለት ነበር፡፡ ባአለ=ባለቤት፤ ጌ=አገር) ለብዙ ዘመን ደብረወርቅ ነበርኩ፡፡ ከዝያ ወደ ሸዋ ሄድኩ፡፡ ከዝያም አሥረው ወደዚህ አመጡኝ፡፡
መርማሪ- በእግዚአብሄር ስም ፤ከምን ትውልድ እንደሆንክ እውነቱን ንገረን
ጃንሸላሚ- ከነገደ ዣን ሸላሚ ነኝ…የወርቅ የብርና የብረት ሥራ በተቻለኝ መጠን እሠራ ነበር፡፡ እንዲህ ስኖር ለምግብና ለልብስ የሚሆን ገንዘብ አጥቸ ተቸገርሁ። ድህነት ሲጠናብኝ ቅድም እንደነገርኳችሁ ምግቤን የማገኝበት ሥራ ፍለጋ ወደ ሸዋ ሄድኩ“
ጃንሸላሚ ይህንን ከተናዘዘ በኋላ ሳይገባው ለመንገሥ በመቃጣቱ ተወንጅሎ በስቅላት ተገደለ፡፡ ብርቅ ያንጣሪነት ችሎታውም አብሮት ዛፍ ላይ ተንጠለጠለ፡፡
እስከዛሬ ድረስ ጥቂት የማይባል ያገሬ ሰው ለፍቶ ፤ በላቡ እንጀራ በልቶ ቤት ሠርቶ “ አንቱ” ተብሎ መኖር እንደማይችል ያውቃል፡፡ ስለዚህ ከተቻለ ጠቅላይ ምኒስተርነትን ፤ካልተቻለ የቀበሌ ሊቀመንበርነትን በትረ ስልጣን ለመጨበጥ ይዋደቃል፡፡ጃንሸላሚነት ካላዋጣ ወደጃንሆይነት ለመሻገር መሞከር ያባት ነው፡፡
አንሸወድ! ለፍቶ አዳሪውን ከጥቅምና ከመታሰቢያ ማግለል ያገራችን ብቻ ሳይሆን የሠይፍ አምላኪዋ ዓለማችን ዓመል ነው፡፡ ብሬሽት የተባለው ጀርመኔ ከጻፈው ዝነኛ ግጥም የትርጉም ትርጉም ጠቅሼ ላጥ ልበል!!
Young Alexander conquered India.
He alone?
Caesar beat the Gauls.
Was there not even a cook in his army?
አፍለኛው እስክንድር ህንድን አስገበረ
ብቻውን ነበረ?
ቄሳርም ጎሎችን ድባቅ ሲመታቸው
ወጥ ቤቷ ተረሣች
ለዘማቾች ራት የሠራችላቸው

The post ከጃን ሸላሚነት ወደ ጃንሆይነት!(በ.ሥ) appeared first on Zehabesha Amharic.


የዛሬው የኢትዮጵያ ችግር ተጠያቂው ማን ነው –ሰርጸ ደስታ

0
0

UDJ-Ethiopia.jpgብዙ ጊዜ ሳስተውል በተለይ በኢትዮጵያ የቅርብ ጊዜ ታሪክ ለነገሮች ተወቀሽ የሚሆኑት በስልጣን ላይ ያሉና የነበሩ ግለሰቦች ወይም የእነሱ አገዛዝ ብቻ ናቸው፡፡ በተቃራኒው እነዚህን ባለስልጣናትና አገዛዛቸውን የተቃወመ ብዙ ጊዜ ይወደሳል፡፡ በታሪክ ውስጥም ትልቅ እይታ ተሰጥቷቸው የሚነሱት ገዥና ተቃዋሚ ጎራ ላይ ያሉ ናቸው፡፡ ከታሪክ እንደምናየው እነዚህ ሁለቱም የየራሳቸው ጉድለት ያለባቸው ማስተዋላቸውን ስሜታዊነትና እኔ እበልጥ የሸፈነባቸው፣ ውሳኔዎቻቸውና ድርጊቶቻቸውም የራሳቸውን ምኞት እንጂ የአገርንና ሕዝብን የማይወክል ነው፡፡ ከእነዚህ ከሁለቱ ውጭ ሆነው ግን በሰከነ አስተሳሰብና ፍልስፍና ከቀደሙና ካሉ ነባራዊ ነገሮች ተንተርሰው የነገሮችን መጻኢ ሁኔታ የሚተነብዩና አቅጣጫንም መሆን በሚገባው የሚጠቁሙ ቦታ አይሰጣቸውም፡፡ ኢትዮጵያ በተለይም ከ50ዎቹና 60ዎቹ ጀምሮ እስከዛሬም ድረስ የራሳቸው ስሜት፣ ዝናን፣ ስልጣንና ገንዘብ ያሳበዳቸው የአገርና ሕዝብ ጉዳይ ከአእምሮአቸው የነጠፉ ሰዎች ሀሳብና ፍላጎት መመራቷ ብቻም ሳይሆን ለወደፊት የእነዚሁ ልክፍቶች ሰለባ መሆኗ አእምሮ ላለው ያማል፡፡ ሕዝብና አገር መነገጃ ሆነዋል፡፡ እባካችሁ ይሄ ነገር አይሆንም ብለው የነበሩ ዛሬ በሕይወት የሉም ካሉም ዝም እንዲሉ ተደርገዋል፡፡

እንደእኔ አስተሳሰብ ከ50ዎቹ አጋማሽ ጀምሮ እስከ 70ዎቹ መጀመሪያ ባሉት እንቅስቃሴዎች ተሳተፍኩ እያለ እንደ ትልቅ ነገር የራሱን ዝና ዛሬም ድረስ እየነገረን ያለው ትውልድ ትልቅ የአእምሮ መዛባት ችግር የገጠመው ነው ባይ ነኝ፡፡ እውነታው ይሄ ሆኖ እያለ ከዚህ ትውልድ አስተሳሰብ ያፈነገጠ ሁሉ እንደ እብድ እየታየ ዝጋ ይባላል ወይም የሚያስፈራ መስሎ ከታየም ለዘላለሙ ይሸኛል፡፡ ዛሬ በዋነኝነት አገርንም የሚመራው፣ እንደተቃዋሚም የሚንቀሳቀሰው የዛ ትውልድ ነው፡፡ ጥሩና ትክክል የሚያስቡት አሁንም እድል አልቀናቻቸውም፡፡ እና ማን እያሰበ አገርና ሕዝብ ሠላም ሊሆኑ እንደሚችሉ ሳስብ ግራ እጋባለሁ፡፡

የዛን ትውልድ እንዳንድ ባሕሪያት ለመጠቆም

  1. ስብዕና የሌለው ጨካኝ
  2. እምነት ከአላቸው ወላጆች ተወልዶ ሐይማኖት የሌለው ከሀዲ
  3. ተቃዋሚሕን አጥፋ ነገ ሊያጠፋሕ ይችላል በሚል ፍልስፍና የተለከፈ ፈሪና ተጠራጣሪ
  4. ራሱን ምሁርና አዋቂ ያደረገ በሌሎች ፍልስፍና የባርነት አዘቅት የወደቀ
  5. የሌሎችን የሚናፍቅ መሠረቱን ያላወቀ
  6. የአገርና ሕዝብን ለራሱ ጥቅም መሳሪያ ያደረገ የሕዝብና አገር ጠላት
  7. ራሱን ዝነኛ ለማድረግ እስከሞት ድረስ የሚንፈራገጥ
  8. አመክንዮ (ሎጂክ) የሚባል ነገር የሌለው ግትርና ነባራዊ ነገሮችን ለማሰብ አምቢ ያለ
  9. ውሸታምና ውሸትንም በመደጋገም እውነትን ከሰው አእምሮ የሚያምከን የመሳሰሉት

ይህ ከላይ የዘረዘረኩት የእኔ እይታ እንጂ ትክክል ላይሆን ይችላል፡፡  በእኔ ግንዛቤ ስልጣን ላይ ወጣም አልወጣም፣ ተቃዋሚ ሆነ ገዥ ተማርኩ የሚለው አብዛኛው የዛ ትውልድ  ዛሬ ኢትዮጵያ ለገባችበት ምስቅልቅል ተጠያቂ ነው ባይ ነኝ፡፡ የቀደመውም በኋላም የመጣው ግን ሙሉ በሙሉ ነጻ ነው ማለቴ አይደለም፡፡

ዛሬ የምንሰማው አብዛኛው ድምጽ ንጉሱን በወቅቱ የተቃወመው የዛ ትውልድ ስለሆነ በወቅቱ እውነታው ምን እንደነበር መረዳትም ያስቸግራል፡፡ የንጉሱ የአገዛዝ ዘመን ብዙ ጉድለቶች ሊኖሩት እንደሚችሉ አልጠራጠርም፡፡ በእርግጥም እነዚያ ጉድለቶች በወቅታቸው አለመደፈናቸው ምክነያት ሆነው ዛሬ ድረስ ለቀጠለው የአገርና ሕዝብ ጉዳይ የማይገባው በዛ ትውልድ እጅ አገር እንደወደቀች አምናለሁ፡፡  ከእነዚህ አንዱን መሬትን እንውሰድ፡፡ የመሬት ይዞታ ጉዳይ የንጉሱ ፍላጎት ብቻም ሊሆን እንደማይችል እገምታለሁ፡፡ ይልቁንም የአደገኛ ባላባቶች ለጉዳዩ መላላትን ያለማሳየትና በሕዝብ ላይ በፈጸሙት የአገዛዝ ጫና እንጂ፡፡ ሆኖም በቆይ የሄ ጉዳይ በሌላ መልኩም ቢሆን እልባት እንደሚያገኝና ንጉሱም ለዛ ያሰቡበት ይመስለኛል፡፡ ዛሬ ዓለም ላይ ብዙ አገራት የመሬትን ይዞታ ጉዳይ የፈቱት እኛ በሄድንበት መንገድ አይደለም፡፡ ይልቁንስ እኛ የተከተልነውን አይነት መንገድ የተከተለ ለመኖሩ እርግጠኛ አይደለሁም፡፡ እንደውም መሬት በእነዛው ድሮ በነበሩ ባለመሬቶች እንደ ተያዘ ነው ለውጡ ከአንዱ የምጣኔ ሀበት እድገት ወደሌላው የተሸጋገረው፡፡ የፊውዳሉን የአገዛዝ ሥርዓትም እጅግ ያከፋነው እኛ እንጂ ከሌሎች አገራት የከፋ ሆኖ አይመስለኝም፡፡ የሥርዓት ሽግግራቸው ግን እንደ እኛ ሥር ነቀል አይደለም፡፡ ሌላ ቀርቶ የታወቁ አብዮቶች የተካሄደባቸው አገራት ድሮ የነበረውን ሙሉ በሙሉ የለወጠም አይደለም፡፡ ዛሬም ድረስ የዛ ሥርዓታቸው ቅሪት ይዘው እየተጓዙ ነው፡፡  ሥር ነቀል የተባለለት የእኛው ግን የታሰበውንም ለውጥ ሳያመጣ የአገርን መሠረት ያናጋ እስካሁንም በሁለት እግር መቆም የላስቻለን፣ ይልቁንም እየከፋ የመጣ ነው፡፡

ከመሬት ውጭ ያሉ ለውጦች ጭራሽ አገርንና ሕዝብ የማይፈልጓቸው ያ ትውልድ ለራሱ እንዲመቸው ሆን ብሎ ያመጣብን አደጋዎች እንደሆኑ በደንብ ከውጤታቸው እያየን ነው፡፡ የፌደራሊዝም ጥያቄ፣ የብሔረሰብ ጥያቄ፣ የሴቶች፣ የወጣቶች ወዘተ የሚባሉት ሁሉ የአገርና ሕዝብ ሳይሆኑ ያ ትውልድ ለራሱ እንዲመቸው ያመጣብን መርዞች ናቸው የሚል እምነት አለኝ፡፡ አገርና ሕዝብ ፍትሕን፣ መልካም አስተዳደርን፣ ድህንነትንና ልማትን ነው የሚፈልገው፡፡

እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ እኔ በአደኩበት ሥፍራና ሁኔታ ብዙም ያልተረዳሁት ግን የብሔረሰብን ጥያቄ የመሳሰሉ ጉዳዮች በሌላ አካባቢ የሕዝብ ጉዳይ ሳይሆን አይቀርም የሚል ግምት ነበረኝ፡፡ ኋላ ግን እድሉ ገጥሞኝ አገሪቱን ሙሉ በሙሉም ባይሆን ቢያንስ ከግማሽ በላይ በተለያይ አጋጣሚዎች ስንቀሳቀስ እንዳየሁት የብሔረሰብ ጥያቄ ከነጭርሱም የሕዝብ ችግር አልነበረም፡፡ ይልቁም ሕዝብ በተለይ በእድሜ ጸና ያሉ አረጋውያን ይሄ አሁን በእናንተ ዘመን የመጣብን ችግር ነው እያለ ያመጣባቸውን ትውልድ ሲወቅስ እናስተውላለን፡፡ ልብ በሉ መፍትሔ የተባለው ሲጀምር ችግሩ በሌለበት ነው አሳዛኙ ደግሞ ላልነበረ ችግር መፍትሄ በሚል በሕዝብ ዘንድ ግን ችግር የሆነውን መተግበር ነው፡፡ ሁሉም የኢትዮጵያ አካባቢ ብትሄዱ በሚኖርበት አካባቢ ሕዝቡ ባሕሉንም፣ ቋንቋውንም እንደልቡ ነው የሚጠቀመው፡፡ በቋንቋውና በባሕሉ የሚያፍር ሕዝብ አልገጠመኝም፡፡ ችግሩ ከተለያየ ሕዝብ ወጥተው ት/ቤት የተገኛኙ ተማሪዎች እንደነበር አሰብኩ፡፡ እዛው ት/ቤት ተወልዶ አብሯቸው ዩኒቨርሲቲ የዘለቀ የበታችነትና የበላይነት ስሜት የብሔረሰብ የምትል ጥያቄ እንዳመጣ ተረዳሁ፡፡ ጥያቄው የሕዝብ እንዳልሆነም፡፡ በቅርቡ ከኤስቢኤስ ራዲዮ ጋር ቃለምልልስ ያደረጉት ፕ/ር ዓለም ሀብቱ ጥያቄው ከእነጭርሱ የኤርትራን ሕዝብ ለመደገፍ በሚል እንደተነሳ ይነግሩናል፡፡

አየር ላይ ከዋለ የቆየ ቢሆንም እኔ በዚህ ሳምንት ያየሁት የሚከተለው ሊንክ ላይ የምንሰማው ሰው(ሥሙን ማወቅ አልቻልኩም፣ ከይቅርታ ጋር የተናጋሪውን ሥም የሚያውቅ ቢነግረኝ እላለሁ) አስበው የነበረውን ሁሉ ሲናገረው ስሰማ ከማሰብም አልፈው ብዙ የለፉ እንደነበሩ አስቤ እራሴንም ታዘብኩ፡፡ https://www.youtube.com/watch?v=sz3M9jiwx0w

ተናጋሪው በ60ዎቹ እንቅስቃሴ ተሳታፊ የሆነ ዕድሜ ያለው አይመስልም፡፡ የሚያወራው ግን የሟች ጠ/ሚኒስቴርን መለስን ጨምሮ አብዛኛው የስልሳዎቹ ለሆኑት ተሰብሳቢዎች ነው፡፡ ተናጋሪው እኔ ነብይም ወልይም አደለሁም ይላል፡፡ ልሆን የሚችለውን አደጋ ግን ከሩቅ ሆኖ ወደፊት መተንበይ ነብይ አለመሆኑ አላገደውም፡፡ የሚናገረውም  በዘመናት ከአያቸው ነባራዊ እውነታዎችና ልምዶቹን መሠረት አድርጎ እንጂ ጥሩ ተናጋሪ ለመባል፣ ለመደነቅ አይደለም፡፡ እንዲያ ሲሆን በእርግጥም ነብይም ባይሆኑ ወደፊቱን መተንበይ ይቻላል፡፡ አእምሮ ውሸት አይናርምና፡፡ የ60 ትውልድ ትሩፋት የሆነው የብሔረሰብን ጥያቄን በሚል አቶ መለስን ጨምሮ ብዙ የ60ዎቹ የሚመሩት ኢሕአዴግ በፖሊሲ አስፍረው የጎሳ ፌደራሊዝም የተገበሩት ፖሊሲ ቆይቶ ችግር ሊሆን እንደሚችል ተናጋሪው ከመጠቆምም አልፎ እየደጋገመ አስጠንቅቋል፡፡ ይህ ተናጋሪ እንደ 60ዎቹ ትውልድ የማንነት ጥያቄና የበታችነት ስሜት ፈጽሞ አይታይበትም፡፡ የሚናገረው በሙሉ ልብና ፍጹም በተረጋጋ ሁኔታ ፊት ለፊት ነው፡፡ በብሔረሰብ ሥም የተደራጁ አሸን የሆኑት የፖለቲካ ድርጅቶቻችን መሪዎች አሁንም ልክ ነን ይሉናል፡፡ እረ እንደውም የዚሁ የ50-60ዎቹ ምሁራንም እንዲሁ እንደሚያስቡ እናደምጣለን፡፡ በኤሰቢኤስ ራዲዮ የሰማናቸው ፕ/ር ገብሩ ታረቅ በጎሰኝነት ላይ የተመሠረተውን የኢትዮጵያ ፌደራሊዝም አሁን ሥልጣን ላይ ያለው ኢሕአዴግ ለአገሪቱ ያበረከተው ትልቅ ለውጥ ሲሉ ኢሕአዴግን ያወድሉ፡፡ ኢሕአዴግ አሁን የገጠሙት ፈተናዎች መሠረቱ ይህን የመሠለ የፌደራል ሥርዓት ዘርግቶ ሥርዓት ላይ አለማዋሉ ነው ሲሉ ይመክራሉ፡፡ ገብሩን በወቅቱ ስለሰጡት ቃለ መጠይቅ ብዙ ቦታ እንደወደድኩላቸው ባለፈው ጽሑፌ ተናግሬአለሁ፡፡ የአገርና ሕዝብ አደጋ ሆኖ የሚታየውን ብሔርን መሠረት ያደረገውን ኢትዮጵያን የበከፋፈለ የኢሕአዴግን ፌደራሊዝም ማወደሳቸው ግን መስሏቸው ነው ብሎ ለማለፍ እንኳን ይከብዳል፡፡ ገብሩ ምሁር ናቸው፣ በዚህ ላይ ሂደቱን የሚያስተውሉና የሚከታተሉ የታሪክ ምሁር፣ ከዛም በላይ አሁን እየሆነ ያለው ነባራዊ እውነታ ምስክር ሆኖ ሁሉ በግልጽ የሚረዳውን ችግር ሆን ብለው የሕዝብን ግንዛቤ ለማንሻፈፍ ምሁርነታቸውን ተጠቅመው የተናገሩት እንዳይሆን እፈራለሁ፡፡ ከተሳሳቱ ችግር የለውም፡፡ እኔም አሁንም አላለሁ ገብሩ ተሳስተዋል፡፡ ሆን ብለው ከሆነ ግን ይቅርታ እንዲጠይቁንም እፈልጋለሁ፡፡ ካለሆነ እባብ ሞኝን ሁለት ጊዜ ነደፈው አንዴ ሳያውቅ ሌላ ጊዜ መንገድ ከጓደኛው ጋር ሲሄድ የነደፈኝ ነገር ይሄ ነው ብሎ  ተጠቅልሎ የተኛውን እባብ በጣቱ እይነካ ለጓደኛው ሲያሳይ ነደፈው ይባላል፡፡ ከላይ የምታዩት ተናጋሪና ብዙ ሌሎች ቀድሞም ሊሆን የሚችለውን በደንብ እንረዳው ነበር፡፡ ዛሬ ግን በአየን የሚታየውን እውነት ሁሉም ይረዳዋል፡፡

የኢሕዴግና ደርግ የ60ዎቹ ትውልድ ሥርዓት ተደምሮ ዛሬ ንጉሱ መሪ ከሆኑባቸው 43 ዓመት ጋር እኩል ሆኗል፡፡ በአገር ላይ ያመጡት እድገት ግን የንጉሱን ዘመን ያሕል አይደለም፡፡ ይህን ሥል አሁንም እንዳይንሻፈፍ ኢሕአዴግ ብዙ ለውጥ እንዳመጣ ይታሰባል በእርግጥም ከደርግ በተሻለ ለውጥ ለማመጣቱ አያከራክርም፡፡ ከንጉሱ ዘመን ጋር ግን ሲወዳደር ለውጡ ደካማ ነው የሚል እምነት አለኝ፡፡ ልብ በሉ ንጉሱ ከምንም ተነስተው ብዙ ዛሬ ድረስ የምናያቸውን ዘመናዊ ልማቶች እንደሰሩ እናስተውል፡፡ አዋሳና ባሕርዳርን ጨምሮ ሌሎች ከተሞች ንጉሱ የመሠረቷቸው ብቻም ሳይሆን በዘመናዊ ፕላን እንዲያድጉ መሠረት ጥለዋል፡፡ አዲስ አበባ ውስጥ ዛሬ ድረስ ውብ ሆነው የምናያቸው ሕንጻዎች በንጉሱ ዘመን የተሠሩ ናቸው፡፡ በነገራችን ላይ አሁን ብዙ ሰው የሚያደንቀው የኢሕአዴግ ዘመን የአዲስ አበባ ሕንጻዎች ምን አልባትም ለወደፊት የከተማው ችግር እንዳይሆኑ እሰጋለሁ፡፡ ጥንካሬአቸውና ሌላ ጥራታቸው በእድሜ ብዛት የሚያደረሰው ጉዳት እንዳለ ሆኖ እየተጠቀሙት ያለው መስታወት ጨረሮችን ወደሕዝብና አካባቢው በመርጨት ለጤና አልፎም እጽዋትን ጨምሮ ሌላ ሕይወት ላይ አደጋ ሊሆን ይችላል ሲሉ የሚያስጠቅቁም አሉ፡፡ መስታወት መሆኑ ሳይሆን የመስታዎቶቹ ጥራት ደረጃ ነው፡፡ የሕንጻዎቹን ጥራት ግን አሁንም ሰንበት ባሉት እያየንው ያለ ነው፡፡ በንጉሱ ጊዜ የተሰሩት ዘመን አልፎ ዛሬም ድረስ ውበታቸውን እናደንቃለን፡፡ ዛሬ የሚሰራው ግን ከ10 ዓመት በኋላ ብናየው መስታወቶቹ ረግፈው፣ ግድግዳው ተንዶ ሊታይ ሁሉ ይችላል፡፡ በዚህ ላይ ብዙዎቹ ፕላናቸው ራሱ አጠያያቂ ነው፡፡ ለማስተዋል የብሔራዊ ባንክን ጨምሮ፣ ፖስታ ቤትን፣ ለገሀር፣ መስቀልአደባባይ አራት ኪሎ፣ መዘጋጃ ቤት የመሳሰሉትን የንጉሱን ዘመን ሕንፃዎች አስተውሉ፡፡

ሌላው አድስ አበባ ውስጥ በቅርብ በቻይና ከተበረከተልን የጥሩነሽ ዲባባ ቤጂንግ ሆስፒታል ውጭ ሁሉም የመንግስት ሆስፒታሎች መንጉሱ የተሰሩ መሆኑን ስንቶቻችን ታዝበናል;

ከአዲስ አበባ ውጭም የዘመናው የግል እርሻዎችን ጨምሮ ብዙ ልማቶች በንጉሱ ዘመን የተሳካላቸው ነበሩ፡፡ አሁንም ደርግን ልረሳው ነው፡፡ ምን እንደሰራም አይገባኝም፡፡ ኢሕአዴግ በተለይ ከ10ዓመት በኋላ ብዙ መንገድንና የጤና ተቋማትን፣ ትምህርት ቤቶችን በመገንባት ጥሩ ለውጥ አምጥቷል ከሚሉት ነኝ፡፡ ከዜሮ ከተነሱት ከንጉሱ ጋር ግን ሲወዳደር ብልጫ ካለውም ብዙ የሚባል አይመስለኝም፡፡ በመንገድ ግን ግልጽ የሆነ ብልጫ አለው ባይ ነኝ፡፡ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማትን አስመልክቶ አሁን ቁጥሩ እምርታ ያለው ቢሆንም ብዛቱን በቅርብ ነው የሠራቸው፡፡ መገንባታቸው መልካም ሆኖ ዕቅድ ላይ ተመስርቶ ለመሆኑ እጠራጠራለሁ፡፡ ኢሕአዴግ ልማት የሚሰራው የአገራዊ ኃላፊነት ግዴታው እንደሆነ  አውቆ ሳይሆን የሄን ሠራሁ፣ ይሄን አደረኩላችሁ በሚል ለምርጫ ወይም ለመወደስ ነው የሚመስለው፡፡ ይህ አገርና ሕዝብን የማይወክለው 60ዎቹ ትውልድ አይነተኛ ባሕሪው ነው፡፡ ትንሽንም ትልቁንም እያጋነነ ማውራት ያበዛል፡፡ ለኢትዮጵያ ሕዝብ ምንም ማለት እንዳልሆነ ማሰብ የሚችሉ ባለስልጣናት የሉትም፡፡  በዚሁም ምክነያት ሥራዎች ታቅደው አይሰሩም ወጫቸውም ከተፈጥሮ ወጭያቸው በላይ ነው፡፡  ዛሬ ጥራታቸው ባይሟላም ግን መሠራታቸው በራሱ ጥሩ ነው ባይ ነኝ፡፡

ይህ ሁሉ ማወዳደር ግን እዛው እዛው እንጂ ኢትዮጵያን ከሌላ አገር ጋር አይደለም፡፡ ኢትዮጵያን ከሌሎች ጋር በሚለው ስንመጣ የንጉሱ ዘምን አገሪቱን ከብዙ ዛሬ በኢኮኖሚ አልፈዋት ከሄዱ በላይ የሚያሰፍር ነው፡፡  እንደውም ኢትዮጵያ በንጉሱ ዘመን ከአፍሪካ አገራት ጋር ሳይሆን ትልቅ ሥም ካላቸው እንደ ጃፓን ካሉ አገራት ጋር አኩል የሆነችበትም ወቅት ነበር፡፡ እርግጥ የጃፓን ኢኮኖሚ በሁለተኛው አለም ጦርነት ወድሞ ነው፡፡ አፍሪካ አገራት በወቅቱ አብዛኞቹ ቅኝ ስለነበሩ መወዳደርም አይችሉም፡፡ የሆነ ሆኖ አገሪቱ አሁን ካለችበት በተሻለ በኢኮኖሚ ከአለም አገራት ተወዳዳሪ እንደነበረች አይካድም፡፡ ደርግ ይውደም እያለ ሁሉንም ማወደም ነበር፡፡ በኢሕዴግ የመጣብን ልክፍት ደግሞ እድገቱ ባይካድም ግነቱ አሁን እያሳፈረን መጥቷል፡፡ ኢሕአዴግ ከ1997 ዓ.ም ጀምሮ የአገሪቱ ኢኮኖሚ በየአመቱ በሁለት ዲጂት እያደገ መሆኑን ለ10 ዓመታት ቢያወራም አገሪቱ አንድም እከሌ የምንለውን አገር በኢኮኖሚ ስትበልጠው አልሰማንም፡፡ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እንደውም ሌሎችም አዎ እያሉ እኛው የምንነግራቸውን ይሁንላችሁ አይነት ይነግሩናል፡፡ እንዲህ ያለው ነገር ራስን ከመግደል አሳንሼ አላየውም፡፡ የአገር እድገት በሕዝብ አኗኗር ላይ እራሱ በሚፈጥረው መገለጥ ይታያል፡፡ አሁን የደረሰብንን ድርቅ ጨምሮ አገሩን እየለቀቀ  በሞት በረሃዎች ሳይቀር የሚሰደደውን ዜጋ፣ በብዙ የአገሪቱ ነዋሪዎች የሚታየውንደ ድህነት መረዳት የማይችሉ ራሳቸው በዘረፉት የአገርና ሕዝብ ንብረት የደለቡ የ60ዎቹ ትውልድ ባለስልጣኖችና አባሮቻቸው እድገቱን የሚያዩት በራሳቸው ኑሮ ስለሆነ ይመስለኛል፡፡

በአጠቃላይ በእኔ ግንዛቤ ያ የ50-60ዎቹ ትውልድ ብዙ አስተሳሰቡ የግል ምኞትና ጥቅም ያየለበት፣ ካልሆነም ሌሎችን መሆን የሚናፍቅ ኢትዮጵያንና ሕዝቧን የማይወክል አስተሳሰብ ያለው ነው ባይ ነኝ፡፡ አሁንም ቢሆን ተቃዋሚም በሉት ገዥው ፕለቲካ የሚመራው በዚህ ትውልድ መሆኑ የአገርና ሕዝብ ጉዳይ መፍትሔ አለማግኘቱ ሳያነስ ከግዜ ወደጊዜ እከፋ መሄዱ አሳሳቢ ነው ባይ ነኝ፡፡ ዛሬ 25 ዓመት የሆነው ትውልድ ደግሞ የ60ዎቹ ትውልድ ያመረተው እንደሆነ ጭምር ሳስብ ስጋቴ የጎላል፡፡ በመሀል ያለው ተውልድ የተሻለ ይሆን; ይህ የእኔ ሐሳብ ነው ሌሎችስ ምን ይላሉ;

 

እግዚአብሔር አገራችንን ኢትዮጵያን ሕዝቦቿን ይጠብቅ! አሜን!

 

ሰርጸ ደስታ

 

ትክክለኛውን ቴዲ አፍሮን ምን ያህሎቻችን እናውቀዋለን?

0
0

teddy-afrio2.jpg

(ኤርሚያስ ቶኩማ)
ብዙዎቻችን ቴዲ አፍሮን ከሙዚቃ ሥራውና ከሐገር ወዳድነቱ ባሻገር እምብዛም የግል ሕይወቱን እና ምን አይነት ሰው እንደሆነ አናውቀውም እርሱም ቢሆን ስለራሱ ማውራት ስለማይወድ እና ይህንን ፈፀምኩኝ ብሎ ስለማያወራ የቴዲን ማንነት በግልጽ ልናውቀው አልቻልንም ሆኖም ቴዲ አፍሮ እንደዚህም አይነት ሌላ ገፅታ አለው።
★ ሐምሌ 30,1998 ዓመተ ምሕረት በድሬዳዋ ደርሶ በነበረው የጎርፍ አደጋ ለተጎዱ ወገኖች የ30 ሺህ ብር ድጋፍ በማድረግ
ለወገን ደራሽነቱን አሳየን።
★ ጥቅምት 1,2002 Elshaday relief and development ባዘጋጀውና ከ50 ሺህ በላይ በተገኘበት የአዲስ አበባ ስታዲየሙ
ኮንሰርት ከ 1 ሚሊየን ብር በላይ አሰባስቦ ለእርዳታ ድርጅቱ ያስረከበ ሲሆን በእለቱ ለአበበች ጎበና ሕፃናት ማሳደጊያ 100
ሺህ ብር ለይልማ ገ/አብ የወርቅ ብእር ሸልሟል።
★ ጥቅምት 23,2002 በህመም ላይ ትገኝ ለነበረችው ማንአልሞሽ ዲቦ መታከሚያ ይሆን ዘንድ 20 ሺህ ብር አበረከተ
★ ጥቅምት 17,2004 የወጣት አስመሮም ሃይለስላሴን ነፍስ ለማዳን ለሶማሊያ ሽማግሌዎች 700 ሺህ ብር ከፈሎ የወገኑን
ህይወት አተረፈ።
★ ጥቅምት 17,2004 ለኢትዮጵያ የአካል ጉዳተኞች ማህበር የ200 ሺህ ብር ድጋፍ አድርጎ ለማህበሩ ያለውን አጋርነት አሳየ። ማህበሩም የምስጋና ምስክር ወረቀት ሰጥቶታል።
★ የአራት ኪሎ ወጣቶች ከአልባሌ ሥፍራ ይርቁ ዘንድ በአባቱ ስም ተቋቁሞ ለነበረው የእግር ኳስ ቡድን ለአራት አመታት በየአመቱ ግማሽ ሚሊየን ብር ድጋፍ አድርጓል።
★ በራሱ አነሳሽነት ለአበበ መለሰ ኮንሰርት በማዘጋጀት የአርቲስቱን ህይወት ከህልፈት ታደገ።
★ ጥቅምት 2005 ቀድሞ ይማርበት ለነበረው ቤቲልሄም ት/ቤት የኮምፒውተር እና የሙዚቃ መሣሪያ ድጋፍ አደረገ።
ይሄ ነው ሌላኛው የቴዲ አፍሮ ገፅታ
በተለያየ ግዜያት በተዘጋጁ ዝግጅቶች ላይ እንደዚሁም እዛው ድረስ በመሄድ ለወይዘሮ አበበች ጎበና እፃናት ማሳደግያ ከመቶ ሺ ብር በላይ የገንዘብ እርዳታ።
ባለቤቱ አምለሰት ባስመረቀችው አረንጋዴ መሬት ዶክመንተሪ ፊልም ምርቃት ላይ በእንጨት ለቀማ ይተዳደሩ ለነበሩ እናት የ 20ሺብር ቼክ ሰታቸዋል።
እንደዚሁም ለተለያዩ ድምፃዊያን ግጥም እና ዜማ በነፃ የሰጣቸውም አሉ:: ይህ ህዝቡ የሚያውቀው ነው ቴዲና ድጋፍ ያደረገላቸው ብቻ የሚያውቁት ብዙ አለ።
ማሳሰቢያ ይህንን ፅሁፍ በድጋሚ የለጠፍኩት አንድ በምርቃና የድሮ መጽሔት ጽሁፎችን እየገለበጠ መፅሀፍ ካሳተመ በዃላ እራሱን እንደደራሲ ቆጥሮ ለመተቸት የሞከረ በጫት የደነዘዘ ወጠጤ በማየቴ ነው።

ወደ አገር ውስጥ የገባው የኤች አይ ቪ መመርመሪያ ኪት ድረጃውን የጠበቀ አይደለም ተባለ (የፍኖተ ዴሞክራሲ ራድዮ አጫጭር ዜናዎች)

0
0

dire
ሚያዚያ 29 ቀን 2008 ዓ.ም.
ርዕሰ ዜናዎች
 ወደ አገር ውስጥ የገባው የኤች አይ ቪ መመርመሪያ ኪት ድረጃውን የጠበቀ አይደለም ተባለ
 ድሬደዋ የጎርፍ አደጋ አጋጠማት
 የሩዋንዳውን አገዛዝ ሲቃወምና ሽብር ሲፈጥ የነበረ ድርጅት ም/ኃላፊ ኮንጎ ውስጥ በቁጥጥር ስር ዋለ
 ለውጭ ኃይሎች የአገር ሚስጥር አሳልፋችሁ ሰጥታችኋል የተባሉና ከቀደሞ የግብጽ ፕሬዚዳንት ጋር ተከሰው የነበሩ ስድስት ሰዎች የሞት ፍርድ ተፈረደባቸው
 በሊቢያ ምስራቃዊ ክፍል የአንድነት መንግስቱን መመስረት አስመልክቶ ድጋፋቸውን ለመስጠት በወጡ ሰልፈኞች ላይ ከባድ መሳሪያ ተተኩሶ በርካታ ሰዎች ሞቱ፤
 በምዕራብ ሊቢያም የአይሲስ ኃይሎች የያዙትን ቦታ ለማስለቀቅ ጦር ተላከ ዝርዝር ዜናዎች

 የወያኔ የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ከፍተኛ ገንዘብ አውጥቶ እንደገዛ የተነገረለት የኤች አይ ቪ አዔድስ መመርመሪያ ኪት ወደ አገር ውስጥ የገባ ቢሆንም ደረጃውን የጠበቀ አለመሆኑ ታውቋል። ከወራት በፊት ባስተላለፍነው የዜና ዘገባ የኤች አይ ቪ ኤድስ በሀገር ውስጥ አለመኖሩና በዚህም ምክንያት የኤድስ ምርመራ ለማካሄድ አለመቻሉን መዘገባችን ይታወሳል።፡ችግሩን ለመቅረፍም አለም አቀፍ የጤና ድርጅትና ግብረሰናይ ድርጅቶች በሰበሰቡትና በለገሱት ገንዘብ የኤች አይ ቪ ኤድስ መመርመሪያ መሳሪያ ተገዝቶ ወደ አገር ውስጥ ቢገባም የደረጃው ኪት ደርጃውን ያልጠበቀና አስተማማኝ መረጃን የማይሰጥ መሆኑ ታውቋል።፡ይህ ደግሞ በመርማሪዎች ላይ የተሳሳተ መረጃ እንዲሰጥ በማድረግ ዜጎችን ላልተፈለገ አካላዊና ስነልቡናዊ ቀውስ እንደሚያጋልጥ የህክምና ባለሙያዎች ይናገራሉ።

 የጎርፍ አደጋ ደጋግሞ የሚያጠቃት ድሬደዋ ሀሙስ ሚያዚያ 27 ቀን 2008 ዓ.ም. በጎርፍ አደጋ መመታቷ ታውቋል። በዚህ የጎርፍ አደጋ የጎርፍ መከላከያ ተብሎ የተገነባው 120 ሜትር ቁመት ያለው ግድብ መፍረሱንም የዓይን ምስክሮች ተናግረዋል። በዚህ የጎርፍ አደጋ የተነሳ በድሬደዋ የንግድ እንቅስቃሴዎች በተወሰኑ አካባቢዎች ላልተወሰነ ጊዜ እንዳይካሄዱ የድሬደዋ ባለስልጣኖች ማዘዛቸው ሲታወቅ ለጎርፉ አደጋ ማስጠንቀቂያም የፖሊስ አባላት ጥይት በመተኮስ የማንቃት ስራ እንዲሰሩ ተጠይቋል። ሐሙስ ዕለት የጎርፉ አደጋ በአራት ሰዎች ላይ አደጋ ማድረሱ ሲታወቅ በንብረት ላይ ያስከተለው ጉዳት ግን አልታወቀም። በድሬደዋ በመልካ ጀብዱ አካባቢ ያለ አንድ ድልድይም በጎርፉ አደጋ መወሰዱ ታውቋል።

 በኮንጎ ዴሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ምስራቃዊ ክፍል ከፍተኛ ግድያና ጭፍጨፋ ሲያካሂድ የቆየውና የሩዋንዳ ነጻ አውጭ ዴሞክራቲክ ኃይሎች የሚል ስም ይዞ ይንቀሳቀስ የነበረው ድርጅት ምክትል መሪ የነበረው ግለሰብ ከአራት ቀናት በፊት ጎማ በተባለችው ከተማ ተይዞ በቁጥጥር የተደረገ ሲሆን ለፍርድ ሊቀርብ እንዲችል ወደ ዋናው የአገሪቱ ከተማ ወደ ኪንሻሳ የተወሰደ መሆኑን የኮንጎ የማስታወቂያ ሚኒስትር ለዜና ምንጮች ገልጸዋል። የሩዋንዳ ነጻ አውጭ ዴሞክራቲክ ኃይሎች የተባለው ግምባር የተፈጠረው በ1986 ዓም በሩዋንዳ ውስጥ እልቂት በፈጸሙና ወደ ኮንጎ በሸሹ የሁቱ ጎሳ አባላት የተቋቋመ ሲሆን ከዚህ በፊት ቀንደኞቹ የድርጅቱ አባላት በዓለም አቀፉ ፍርድ ቤት ፍርድ ቤት ቀርበው ፍርድ የተሰጣቸው መሆኑ ይታወቃል። የኮንጎ ባለስልጣኖች በቁጥጥር ስር ያደርጉትን የድርጅቱን ምክትል መሪ ከዓለም አቀፉ ድርጅት ጋር ቅርበት ላላቸው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ባለስልጣኖች የሚያስረክቡ መሆናቸው ከዚያም ወደ ሩዋንዳ እንደሚወሰድ ተገልጿል።

 ለካታር መንግስት ስለላ አካሂደዋል የግብጽን መንግስት ሚስጥሮች አሳልፈዋል ሰጥተዋል በተባሉ ስድስት የቀደሞ ፕሬዚዳንት ሞርሲ ባልደረቦች ላይ አንድ የግብጽ ፍርድ ቤት የሞት ቅጣት የወሰነ መሆኑ ታውቋል። ሞርሲ በዚሁ ጉዳይ ክስ የተመሰረተባቸው ቢሆንም በአሁኑ ወቅት ፍርድ ቤት የሰጣቸው የሞት ፍርዶች እሳቸውን አይጨምሩም። በግብጽ ሕግ መሰረት ማንኛውም የሞት ፍርድ ተግባራዊ የሚሆነው ቅጣቱ በእስልምና ህግ መሰረት መሆኑንና አለመሆኑን መርምሮ ውሳኔ ለመወሰን ስልጣን የተሰጣቸው ሙፍቲ የተባሉት በውሳኔው ላይ ያላቸውን አስተያየት ከሰጡ በኋላ በመሆኑ የፍርድ ቤቱ ውሳኔ ለሙፍቲው የተላከ መሆኑ ተገልጿል። የሙፍቲው ውሳኔ ሰኔ 11 ቀን 2008 ዓ.ም. የሚታወቅ መሆኑ ተገልጿል። የሞት ፍርድ ቤት የተፈረደባቸው ተከሳሾች ገሚሶቹ ከአገር ውጭ በመሆናቸው በሌሉበት የተሰጠ ፍርድ ሲሆን ውሳኔው በይግባኝ ሊቀለበስ የሞችል መሆኑ ታውቋል።

 የፓሪሱን የሽብር ጥቃት በማካሄድ በኩል ቁልፍ ሚና የነበረ የአብዱልሃሚድ አባውድ ታናሽ ወንድም ያሲን አባውድ ሞሮኮ ውስጥ በቁጥጥር ስር መዋሉ ከዚህ በፊት የተዘገበ ሲሆን ሽብርን የሚደግፍ ንግግር ተናግረሃል በሚል ክስ ተከሶ በሁለት ዓመት እስራት እንዲቀጣ የተፈረደበት መሆኑ ተነግሯል። ጠበቃው ያሲን ወንድሙ ስለፈጸመው ተግባር የሚያውቀው ነገር እንደሌለ ለመከራከር ቢሞክርም የሽብር ተግባርን ደግፏል በሚል ፍርድ ቤቱ የሁለት ዓመት እስራት ወስኖበታል። ሌሎች አምስት ሰዎች በሽብርና በሌላ ወንጀል ስራዎች ከሁለት እስከ አምስት ዓመታት በሚደርሱ የእስራት ቅጣቶች እንዲቀጡ ፍርድ ቤቱ የወሰነ መሆኑም ታውቋል።

 አርብ ሚያዚያ 28 ቀን 2008 ዓ.ም በምስራቅ ሊቢያ በምትገኘው በቤንጋዚ ውስጥ የሊቢያን የአንድነት መንግስት ለመደገፍ የሊቢያ መከላከያ ተቋም በጠራው ስብሰባ ላይ የከባድ መሳሪያ ሼል ተተኩሶ አምስት ሰዎች መሞታቸውና 11 ሰዎች መቁሰላቸው ተዘግቧል። ከባድ መሳሪያው የተተኮሰው ከከተማው በስተሴሜን ካለ ቦታ ወታደራዊ ተቋሙን በሚጻረሩና የአንድነት መንግስቱን መቋቋም በማይደግፉ ኃይሎች መሆኑ ተነግሯል። ላለፉት ሁለት ዓመታት በተለያዩ ታጥቂዎች ስር የወደቀችው የቤንጋዚ ከተማ ከፍተኛ ውጥረት የነገሰባት ከተማ ስትሆን በተደረጉ የእርስ በርስ ግጭቶች በርካታ ነዋሪዎች መሞታቸው ይታወቃል። በጀኔራል ከሊፋ ሃፍታር የሚመራው የሊቢያ ወታደራዊ ተቋም በርካታ ቦታዎችን ከታጠቁ ኃይል ቁጥጥር ነጻ ያወጣ ቢሆንም ገና ብዙ የሚቀረው መሆኑ ታውቋል።

በተያያዘ ዜና በምዕራብ ሊቢያ ከሚስራታ ከተማ 120 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የሚገኘው አቡ ግሬን የሚባለው መስቀለኛ መንገድ በአይሲስ ኃይሎች ቁጥጥር ስር በመወደቁ ቦታውን ለማስለቅቀ ከሚስራታ የሚሊሺያ ኃይሎች የተንቀሳቀሱ መሆኑ ተነገሯል፡፤ ሐሙስ ሚያዚያ 26 ቀን የአይሲስ ኃይሎች በቅድሚያ አጥፍቶ ጠፊ ባፈነዳው ቦምብ ሁለት ፖሊሶችን ከገደሉ በኋላ ባካሂዱት የተጠናከረ ጥቃት ቦታውን ለመቆጣጠር የቻሉ መሆናቸው ታውቋል። በሚስራታ የሚገኙ ሆስፒታሎች ካስተላለፉት መርጃ በውጊያው 8 ዜጎች መሞታቸውና 105 የሚሆኑ የቆሰሉ መሆናቸው ለማወቅ ተችሏል። በሚስራታ የሚገኘው የወታደራዊ ካውንስል መሪ በስራቸው የሚገኙት ወታደራዊ ብርጌዶች ወደ ቦታው ተንቀሳቅሰው አካባቢውን ነጻ እንዲያወጡ ትእዛዝ መስጠታቸውን አስታውቀዋል። የአይሲስ ቡድን ባለፈው ዓመት ሰኔ ወር ላይ ሰርት የተባለችውን ከተማ በመቆጣጠር የማሰልጠኛ ካምፑን ያጠናከረ መሆኑ ይናገራል። 5000 አባላት እንዳሉት የሚገመተው አይሲስ በሊቢያ እየጠናቀረ መሄዱ ያሳሰባቸው የአውሮፓ መንግስታት አይሲስ ሊቢያን ማዕከል በማድረግ በአውሮፓ አገሮች ላይ ጥቃቱን ያፋፍማል የሚል ስጋት አላቸው።

መሳሪያ የታጠቁ ኃይሎች ጋዜጠኛና ደራሲ ፋሲል ተካልኝን ጥርሱን አወለቁት

0
0

Fasil

በተለያዩ ሚዲያዎች ላይ በጋዜጠኝነት የሚታወቀው ደራሲና ጋዜጠኛ ፋሲል ተካልኝ መሳሪያ የታጠቁ ኃይሎች ክፉኛ እንደደበደቡት አስታወቀ:: ፋሲል በፌስ ቡክ ገጹ ላይ ገጠመኙን እንዳሰፈረው ከሆነ በድብደባው ጥርሱን አጥቷል::

ገጠመኙን እንደወረደ አንበቡት:-

እንዲህ ሆነላችሁ፡፡
ሚያዚያ 6 ቀን 2008 ዓ/ም በግምት ከምሽቱ 4 ሰዓት (ከአዲስ አበባ ሬስቱራንት ጀርባ) አዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን አቅራቢያ አካባቢ መሣሪያ ያነገቱ አምስት ሰዎች ተረባርበው ደበደቡኝ፡፡ራሴን ሳትኩ፡፡ከዚህ በኋላ የሆነውንና የተደረገውን አላውቅም፡፡ ስነቃና ራሴን ሳውቅ ሆስፒታል ውስጥ ድንክ አልጋ በመሰለና ቁመቱ በረዘመ ስትሬቸር ላይ ተኝቼያለሁ፡፡ በግራ እጄ አይበሉባ ግሉኮስ ተሰክቷል፡፡ ማን አመጣኝ? ፣ እንዴት መጣሁ? ለማስታወስ ሞከርኩ፡፡ ዳሩ ግን ማስታወስ የቻልኩት ራሴን እስክስት የነበረውን ብቻ ነው::

በነጋታው ሆስፒታል የተኛሁበት ተኝቼ ካለሁበት ድንገተኛ ክፍል ድረስ በመምጣት ሲናገር እንዳደመጥሁት የፖሊስ ቃል ከሆነ ሸራተን ምግብ ቤት አካባቢ መንገድ ላይ ወድቄ እንዳገኙኘኝና ወደ ራስ ደስታ ዳምጠው ሆስፒታል ይዘውኝ እንደመጡ ነው፡፡ ማለዳ ላይ የተለያዩ ወጣት ሐኪሞች የተካተቱበትና በአንድ አንጋፋ ሐኪም በሚመራ ቡድን ተጎበኘሁ፡፡ በጉብኝቱ መሪ ሐኪም ምን እንደሚሰማኝ ተጠየቅሁ፡፡ምላሽ ሰጠሁ፡፡ ጉሉኮሱ እንዲነቀልልኝና ወደ ጥርስ ህክምና ክፍል እንድሄድ ትዕዛዝ ሰጡ፡፡ወጡ፡፡እንደወጡ ወደ ጥርስ ህክምና ተወስጄ ተመረመርኩ፡፡ ተመርምሬም መድኃኒት ታዘዘልኝ፡፡ በመጨረሻም በሕይወት ወደ ቤቴ ለመግባት ችያለሁ፡፡

ይሁን እንጂ በጎድን አጥንቴና በጀርባዬ ላይ ከባድ ጉዳት ደርሷል፡፡ ሆስፒታል እስክወሰድ ድረስ መንገድ ላይ ወድቄ በነበርኩበት ሰዓት ብዙ ደም ፈሶኛል፡፡በዚህም ምክንያት እስካሁን ያዞረኛል፡፡ሁለት የግራና የቀኝ የላይኛው መንጋጋ ጥርሶቼ ተነቃንቀዋል፡፡ የላይኛውና የፊት ለፊቱ አራት ሰው ሰራሽና ከታች የሚገኙ ሁለት የፊት ለፊት በድምሩ ስድስት ጥርሶቼ ሙሉ ለሙሉ ወልቀዋል፡፡
በተጨማሪም በወቅቱ አድርጌ የነበረውን ሸራ ጫማን ጨምሮ ለጡዘት ቁጥር 2 የግጥም መድበል የተሰናዱ የተለያዩ ግጥሞችና ሌሎች ጽሑፎችን የያዘውን ተንቀሳቃሽ ስልኬን በሺዎች የሚቆጠር ገንዘብ ( ጥቂት የተለያዩ ውጭ ሀገራት የገንዘብ ኖቶች ያሉበት) የተለያዩ መታወቂያዎችንና የኤ.ቲ.ኤም ካርድ ይዞ የነበር ቦርሳዬ ተወስዷል፡፡

የሆነው ሆኖ በሀገራችን የዜግነት ክብር ይሉት ሐረግ ያለው በብሔራዊ መዝሙር ውስጥ ነው እንጂ በገሐድ እንደሌለ በተለያዩ አጋጣሚዎች
ከማረጋገጥ ባሻገር መንግስት ተብዬውም ለሥልጣኑና ለሥርዓቱ እንጂ  ለዜጎቹ ጥበቃ እንደማያደርግ እንደዚሁም ደንታ ቢስና ግድ የለሽ መሆኑን አውቃለሁ፡፡ስለዚህ ፍትህ አገኛለሁ ብዬ ማንንም አልከስም፡፡ከማንም መፍትሔ አልጠብቅምም፡፡ በዚህ አጋጣሚ ከዚህ ከሰፊው መንደር መጥፋቴን ተከትላችሁ፣አለመኖሬ አሳስቧችሁ፣በስልክም ሆነ በውስጥ መስመር ለጠየቃችሁኝ በሙሉ ልባዊ ምሥጋናዬን አቀርባለሁ፡፡

በአ.አ አዳማ ፈጣን መንገድ ላይ በደረሰ መኪና አደጋ የ10 ሰዎች ሕይወት አለፈ

0
0

Car accidenet addis ababa

(ዘ-ሐበሻ) ዛሬ ቀትር ላይ በአዲስ አበባ አዳማ ፈጣን መንገድ (ሃይ ዌይ) ላይ በደረሰ አሰቃቂ የመኪና አደጋ ከ10 ሰዎች በላይ ሕይወታቸው ማለፉ ተገለጸ:: እንደ መረጃው ከሆነ በዚህ አሰቃቂ አደጋ የቆሰሉ ሰዎች ቁጥር በይፋ አልተገለጸም::

በኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት ከምንም በላይ ሕዝብን እየጨረሰ የሚገኘው የመኪና አደጋ ሲሆን አሽከርካሪዎች እንደ ጫት እና መጠጥ ያሉ አደንዛዥ እጾችን ተጠቅመው የሚነዱ ቢሆንም መንግስት በነዚህ ነገሮች ላይ ጥብቅ ቁጥጥር አለማድረጉ ለአደጋዎች መባባስ እንደ አንድ ምክንያት ይወሰዳል::

በአዲስ አበባ አዳማ ፈጣን መንገድ ላይ የደረሰው አሰቃቂ የመኪና አደጋ የሞቱት ወገኖች ማንነት እስካሁን አልታወቀም::

የሺዋስ አሰፋና ዳንኤል ሺበሺ ተፈቱ

0
0

yeshiwas

(ዘ-ሐበሻ) ከሁለት ዓመት  በላይ በእስር ቤት ከቆዩ በኋላ አብረሃ ደስታ፡ የሺዋስ አሰፋ፡ ሀብታሙ አያሌው፡ ዳንኤል ሺበሺና አብረሃም ሰለሞን በነጻ እንዲሰናበቱ ፍርድ ቤት ባለፈው ኦገስት 2015 ቢወስንም ችሎት ደፍራችኋል ተብለው የእስር ቅጣት የተጣለባቸው አብረሃ ደስታ; የሺዋስ አሰፋና ዳንንኤል ሺበሺ እስር ቤት እንዲቆዩ መደረጉ አይዘነጋም::

በዚህም መሰረት የ እስር ጊዜያቸውን የጨረሱት የቀድሞዎቹ የአንድነትና የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮች የሺዋስ አሰፋና ዳን ኤል ሺበሺ ዛሬ ከ እስር መፈታታቸውን ለዘ-ሐበሻ የደረሰው መረጃ ያመለክታል::

 

ይህ በ እንዲህ እንዳለ ከነዚሁ ታዋቂ ፖለቲከኞች ጋር ታስሮ የሚገኘው አብርሃ ደስታ እስካሁን በ እስር ላይ ይገኛል:: አብርሃ ደስታ የተጣለበትን ቅጣት የሚጨርሰው የሚቀጥለው ሰኔ ወር ላይ ነው::

“ታሪክ እንደተግባሩና እንደ ተርጓሚው ነው የሚሄደው።” –ልዑል ራስ መንገሻ ስዩም

0
0

ልዑል ራስ መንገሻ ስዩም፤ ስለ የኢትዮጵያ ዲሞክራሲያዊ ኅብረት/ፓርቲ የትግል እንቅስቃሴ ታሪክና አስተዋጽኦዎችን ይናገራሉ።


“ታሪክ እንደተግባሩና እንደ ተርጓሚው ነው የሚሄደው።” – ልዑል ራስ መንገሻ ስዩም


“ደርግ መስከረም ፪ ቀን ሥልጣን እስከያዘበት ጊዜ ድረስ፤ እንደ ሕዝባዊ ወገን ነበር እናየው የነበረው።” –ክፍሉ ታደሰ

0
0


ክፍሉ ታደሰ፤ መሥራችና የቀድሞው የኢትዮጵያ ሕዝብ አብዮታዊ ፓርቲ (ኢሕአፓ) ስለ ድርጅቱ አመሰራረት፣ የትግል እንቅስቃሴ ታሪክና ሚናዎች ይናገራሉ።
“ደርግ መስከረም ፪ ቀን ሥልጣን እስከያዘበት ጊዜ ድረስ፤ እንደ ሕዝባዊ ወገን ነበር እናየው የነበረው።” – ክፍሉ ታደሰ

ያልታሰረ እኮ አይፈታም!

0
0

ከታሪኩ ደሳለኝ

“እሺ ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ግቢችንን እንዴት አየከው?” “ከግቢያቹ እንዴት ነፃ እንደምትወጡ እየሳብኩ ነው” “ተመስገን አንተ እኮ ነህ ያታሰርከው!” “እኔ ታስሬ አላውቅም የታሰረውስ ሥራዐታቹ ነው ያውም እግር ከወርች እኔ የፃፍኩት ሀገሬን ያሰረው ስርአዐታቹና የስራአቱ አባቶች ከያዛቸው ሀገር የመጥፋት በሽታ እንድትፈቱ እንዲሁም ያልታሰሩ ሰዎችና ያልታሰረ ስርዐት እንዲኖር ነው” “ተው እንጂ በእስር ቤት አጥር ውስጥ ሆነህ አልታሰርኩ ትላለክ እንዴ” “በዚህ አጥር ውስጥማ እናተም ታሳሬ ለመጠበቅ ብላቹሁ ካታሰራቹ ስንት አመታቹ እርግጥ ነው በአካል ከዚህ አጥር ውጪ እንዳልወጣ አድርጋቹሁኛል ሃሳቦቼ ግን የሰራቹሁት አጥር አለገደውም አያግደውምም ይህን ማስቆም የሚችል በየሰዎ ጨንቅላት ውስጥ የሚቆም አጥር መስራት ግን አትችሉም” “ተመስገን ሃሳቦችህ ከእስር ሲያስፈታህ እናያለን ሃስቦችግ ከህመምህ ሲያድኑህ እናያለን” “ያልታሰር እኮ አይፈታም”።
Temesgen Desalegn behindbar

ይህን ንግግር የተነጋገሩት ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ እና የዝዋይ እስር ቤት አዛዥ ኮማንደር አሰፋ ናቸው። ሚያዝያ 28/08 ዓም አርብ አለት ተመስገን ድጋሚ ወደ ሆስፒታል መሄድ እንደማይችል “ትሄድ መስሎካል!” ብለው የነገሩ ቀን የተነጋገሩት ነው።
እኛም ተመስገን “አትጠብቁ የነሱ ስልጣን አይደለም ታዘው ነው” ያለንን ሳንሰማ በዚህ ሳምንት ሆስፒታል ይወስዱታል በማለት ከዛሬ ነገ እያልን ሳምንቱን ብንገፋም በመጨረሻው ቀን ህክምና እንደማያገኝ ማውቅ ችለናል።

እሁድ ሚያዛ 30/08ዓም በዝዋይ እስር ቤት ከተመስገን ጋር በጠያቂና በተጠያቂ ቦታ ተቀምጠን እየተነጋገርን ነው። በዚህ መካከል ተመስገን ከተቀመጠበት ሁለት ሰው አልፋ ብሎ ጠይም እርጅም በእስፖርት የጠበደለ ሰውነት ያለው ሰው መጥቶ ተቀመጠ። እኔ ከተሜ ጋር ማውራቴን ቀጠልኩ “ህክምናውስ ቀረ ሰዎቹስ እንዴት ናቸው?” አልኩት “ይህን ግዜ ሁለቱ እቃዬን እየበረበሩ ነው አንዱ ደግሞ ይህው” አለኝ ከተሜ ፈንጠር ብሎ የተቀመጠው ግዙፉ ሰውዬ። አየሁት አየኝ። “ይህ የመረጃ ደህነነት አባል የነበረ ነው” አለኝ ነው በማለት እራሴን ነቀነኩ። እኔ ከተቀመጥኩበት አጠገብ: አንድ ቀጠን ረዘም የለ ሰው መጥቶ በመቀመጥ ከሰውዬው ጋር ማውራት ጀመረ። ጠያቂውን የማውቀው መሰለኝ ጠያቂው የያዘውን እቃ ለተጠያቂው አቀባለው። ወደ ተሜ ዞሬ “እና እንዴት ነው?” አልኩት “የነበረኝን ቁራጭ ወረቀትና እስክርቤቶ ወሰደውብኝል አንገቴ ቆርጠው እስኪወስዱት ደረስ ግን አይስቆሙኝም” አለኝ ደነገጥኩ። አውቃለሁ ለሀገሬ ስል ያለውን ሁሉ ተሜ እስከመጨረሻው እንደሚያደርግ ግን ሲለኝ ደነገጥኩ። ደንግጪም ዝም አልኩኝ። “በል ሂድ እንዳንዳይመሽብህ” አለኝ
ለስንብት ስነሳ የተሜ ዐይኑ ከኔ አለፍ ብሎ የተቀመጠው የመረጃ ደህነት የነበረውን ሊጠየቅ የመጣውን ሰው ሲመለከት አየሁ አይን ተከትዬ ሳይ ሰውዬው ከደረገው ሱሪ ስር አምልጡ የወጣውን የውታደር ዩኔፎርም ወደ ውስጥ ለመደበቅ ሲታገል ተመለከትኩ። አሁን ሰውዬውን አስታወስኩት “አውቀዋለሁ በር ላይ ከሚፈትሹት አንዱ ወታደር ነው” አልኩት ተሜ ምንም አይነት ስሜት ሳይሰማው እራሱን ነቀነቆ አቅፎ ሰለምታ ሰጥቶኝ ሄደ ከጀርባው ተመለከትኩት የደረገው አረንጓዴ ቤጫ ቀይ ጥለት ያለው እስካርቭ እየተወዛወዘች ነው ለቭንዲራወም ለተሜም ከአንገቴ ጉንበስ ብዬ ስላምታ ሰጥቼ ወጣሁ ።

ከእስር ቤቱ ስወጣ ግን የመረጃ ደህንነት አባሉና የጠያቂው ሁኔታ ግራ እያገባኝ ነው።

በዝዋይ እስር ቤት ጠያቄ መጀመሪያ የሚያጠይቀውን ሰው ስም አፅፎ መጥቶ ያስጠራል እንጂ ተጠያቂው ቀደሞ አይመጣም ወይ በስልክ ወይ በሬዲዬ ጠያቂው ካልተጠረ በቀር ቀድሞ አይደርስም ሌላው ደግሞ ጠያቂ ሲመጣ በጠያቂና በተጠያቂ መካከል የሚቆሙት ወታደሮች የመጣከውን ወረቀት ለሚጠሩ ሰዎች እንድትሰጥ ያደርጉሃል እንጂ መጥተክ ከገኘከው ተጠያቂ ጋር እንድታወራ አይፈቅዱልህም እንዲሁም አንድ ጠያቂ የመጣውን እቃ በር ላይ ቢፈተሽም እነዚህ ወታደሮቹም ድጋሚ ፈትሸው ነው ለተጠያቂው የሚሰጠት። እንግዲህ ከለይ የጠቀስኩት ነገሮችን በመረጃ ደህነት አባል ተጠያቂ እና በፍታሽ ወታደር ጠያቂ መካከል ሲፈፀመ አልተመለከትኩኝም።

እንደው የመብት ሁሉ ጌታ ነኝ የሚል ስርዓት እንደዚህ አይነት ነገር ሲፈፅም ስትመለከት ታዝናለህ ትናደዳለህ ትገረማለክ ምን እንደሚሰማህ አታውቀውም። ብቻ የሆነው ሁሉ ሆኖ አንድ ቀን ተሰፋ አደርጋለሁ ሀገራችን ለሚያሰቡ ሰዎች የሰራችውን እስር ቤት ሁሉ እንደምታፈርስ።

በኢትዮጵያ በካንሰር የሚያዙ ህፃናትና አዋቂዎች ቁጥር ለምን ጨመረ?

0
0

ካንሰር ከ100 በላይ የሚሆኑ በሽታዎች የጋራ መጠሪያ ሲሆን በሰውነት ውስጥ አንዱ ሴል ብቻውን ሲስፋፋ የሚመጣም ችግር ነው፡፡ ለዓመታት በኢኮኖሚ ረገድ ዕድገት ያሳዩ ሀገራት ችግር ብቻ ተደርጎ ሲቆጠር የቆየው ካንሰር፣ ዛሬ ላይ ኢትዮጵያን ጨምሮ ዝቅተኛና መካከለኛ የዕድገት ደረጃ ባላቸው ሀገራትም ዋነኛው የጤና እክል ሆኖ ቀጥሏል፡፡
Cancer
እናም በኢትዮጵያ በካንሰርና ተያያዥ በሽታዎች የሚያዙ ሰዎች ቁጥር አሳሳቢ በሆነ መልኩ መጨመሩን የፌዴራል የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡ ሚኒስቴሩ እንደተናገረው በየዓመቱ ከ60 ሺ በላይ ዜጎች የካንሰር ተጠቂ እየሆኑ ይገኛል፡፡ በመጪዎቹ 10 ዓመታትም ማለትም በ2025 አሃዙ ወደ 100 ሺ የማደግ ስጋት ጥሏል ብለዋል፡፡ በሁሉም የካንሰር አይነቶች በኢትዮጵያ 45 ሺ ሰዎች ህይወታቸውን እንደሚያጡ ነው የሚገመተው፡፡ በተለይ በገዳይነታቸው በቀዳሚነት የሚቀመጡት የጡትና የማህፀን በር ካንሰር ብቻቸውን፣ ከ12 ሺ በላይ ዜጎቻችንን ህይወት በየዓመቱ ይቀጥፋሉ፡፡
በአሁኑ ሰዓት በዜጎች ላይ የሚከሰቱ የካንሰር አይነቶች የጡት፣ የማህፀን በር ጫፍ፣ የሽንት ፊኛ መግቢያ ካንሰርና የአንጀት ካንሰር እንደ አደገኝነት ደረጃቸው ተዘርዝረዋል፡፡ ከፕሮስቴት ካንሰር ውጪ ባሉት ሶስቱ የካንሰር አይነቶች ሴቶች በይበልጥ እንደሚጠቁ ነው መረጃዎች የሚናገሩት፡፡ በዚህ መሰረት ሴቶች ከወንዶች ይልቅ በካንሰር የመያዝ ዕድላቸው 67 በመቶ እንደደረሰ ጠቅሰዋል፡፡ በሌላ በኩል በሂውማን ፓፒሎማ (HPV) ቫይረስ አማካኝነት የሚተላለፈው የፕሮስቴት ካንሰርም በርካታ ወንዶችን ለሞት እያበቃ እንደሆነ ተናግሯል፡፡

በአንፃሩ እንደ ሌሎች ሀገራት የትንባሆ አጫሾች ቁጥር፣ በኢትዮጵያ ከ20 በመቶ የማይበልጥ መሆኑን ተከትሎ በሳንባና ተያያዥ የሰውነት አካላት ላይ የሚከሰቱ የካንሰር አይነቶች ዝቅተኛ መሆኑ ታውቋል፡፡ ነገር ግን ይሄ በዓለም አቀፍ ደረጃ ለካንሰር በሽተኞች ሞት የ20 በመቶ ድርሻ አለው፡፡ በኢትዮጵያ በአጠቃላይ ለሞት ከሚዳርጉ ምክንያቶች መካከል ካንሰር የ40 በመቶ ድርሻ ይዟል፡፡

በ2030 ደግሞ የመሪነት ድርሻውን እንደሚይዝ ተጠብቋል፡፡ ያም ቢሆን ብዙዎቹ የካንሰር በሽታዎች ሊታከሙና ፈውስ ሊገኝላቸው የሚችሉ እንደሆኑ ይነገራል፡፡ በኢትዮጵያ ትልቁ ችግር የሆነውም የካንሰር ስጋት ያላቸው ሰዎች፣ በጊዜ ወደ ጤና ተቋም አለመምጣታቸውና ተገቢውን የባለሙያ እርዳታ አለማግኘታቸው ይገለፃል፡፡

በሀገራችን ለ90 ሚሊዮን ሕዝብ የካንሰር በሽታ ህክምና የሚሰጠው፣ በጥቁር አንበሳ ሪፈራል ሆስፒታል ብቻ ነው፡፡ ከአዲስ አበባና ከክልል ከተሞች ወደ ሆስፒታሉ የሚመጡትም ህክምና ለማግኘት ቢያንስ የአንድ ዓመት ቀጠሮ መጠበቅ አለባቸው፡፡ የዚህን ችግር መኖር የሚያረጋግጡት ዶ/ር ኩኑዝ፣ ከበሽታው ባህሪ አንፃር ጊዜ ሲሰጠው፣ በሰውነት ውስጥ ለማሰራጨት ዕድል የሚያገኝ በመሆኑ ሁኔታው አሳሳቢ እንደሆነ አረጋግጠዋል፡፡
በካንሰር ህክምና ስፔሻላይዝድ አድርገው፣ በጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ህክምና ሲሰጡ ከነበሩ አራት ባለሙያዎች መካከል አንዱ በጡረታ መገለላቸውን ተከትሎ፣ በቀሪዎቹ ሶስት ዶክተሮች ብቻ የካንሰር/የጨረር ህክምና ይሰጣል፡፡ የህክምና መሳሪያው ውድነትም አገልግሎቱን በማዳረስ ረገድ ፈተና መፍጠሩን ዶ/ር ኩኑዝ አስረድተዋል፡፡

በአሁኑ ወቅትም የካንሰር በሽታ ህክምናን ፍለጋ ወደ ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል የሚመጡና የገንዘብ አቅሙ ኖሯቸው ማረፊያ ያላገኙ ሰዎች በየኮሪደሩ ለመተኛትና ወረፋቸውን ለመጠበቅ ተገደዋል፡፡ አንድ ለእናቱ የሆነው የጤና ተቋም/ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል/ ከአቅሙ በላይ ከሆነው ችግር ጋር እየታገለ እንደሆነ ተመልክተናል፡፡ ነገር ግን በሽታው በየዕለቱ በውስጣቸው እየተሰራጨና እያዳከማቸው ተራቸውን የሚጠባበቁት ዜጎችም ተስፋ ብቻ ይመስላል ስንቃቸው፡፡

እ.ኤ.አ  በ2012 ብቻ በዓለም 14 ሚሊዮን ሰዎች አዳዲስ የካንሰር ተጠቂዎች ሆነው ሲመዘገቡ፣ በተመሳሳይ ዓት 8.2 ሚሊየኖች ደግሞ በዚህ በሽታ ምክንያት ህይወታቸውን አጥተዋል፡፡ በቀጣዮቹ ሁለት አስርት ዓመታትም ይሄ መጠን በ70 በመቶ ሊያድግ እንደሚችል የዓለም የጤና ድርጅት አስታውቋል፡፡ ድርጅቱ በካንሰር ሳቢያ ለሚከሰቱ ምቶች አምስቱ ተጠያቂ ምክንያቶችን ዘርዝሯል፡፡ እነርሱም ከፍተኛ ክብደት፣ ዝቅተኛ አትክልትና ፍራፍሬ ተመጋቢነት፣ የአካል ብቃት እንቅስቃሴን አለማድረግ፣ ሲጋራ ማጨስና አልኮል ማዘውተር እንደሆኑ አስቀምጧል፡፡

በኢትዮጰያ የህፃናት ካንሰር በሽታ ለምን ጨመረ?

በኢትዮጵያ የካንሰር በሽታ ጭማሪ ለማሳየቱ የተወሰኑ ምክንያቶችን ይዘረዘራሉ፡፡ የታሸጉ ምግቦችና መጠጦች መበርከት፣ ኢንፌክሽን (በተለይ ከHPV ጋር በተገናኘ) የአካል ብቃት አለማድረግ ተጠቃሾች ናቸው፡፡ እንዲሁም በሽታው ዕድሜያቸው በገፉ ሰዎች ላይ የመከሰት ዕድሉ ከፍተኛ መሆኑንም ተጠቅሷል፡፡ በህፃናት ላይ የሚከሰቱ የካንሰር አይነቶች በአዋቂዎች ላይ ከሚከሰቱት አንፃር የተለዩ መሆኑን ባለሙያዎች ይገልፃሉ፡፡ የደም ካንሰር፣ የዕጢ ካንሰርና የአጥንት ካንሰር ዋና ዋናዎቹ ናቸው፡፡ ቀሪዎቹ የካንሰር አይነቶች በህፃናት ላይ ያለመከሰት ዕድል ቢኖራቸውም አልፎ አልፎ ተከስተው ይታያሉ፡፡

የአጥንትና የደም ካንሰር የሆነው ሉኪሚያ/Leukemia/ ደግሞ በዓለም አቀፍ ደረጃ በህፃናት ላይ የመከሰት ዕድሉ 30 በመቶ ሆኗል፡፡ በሽታው በፍጥነት የመሰራጨትና በህመምተኛው ላይ ድካም፣ መድማት፣ ክብደት መቀነስ፣ የአጥንት ህመምና ሌሎች ምልክቶች አሉት፡፡ በሽታው መኖሩ እንደታወቀም በአፋጣኝ የኬሞቴራፒ ህክምናን መከታተል መጀመር እንዳለባቸው ባለሙያዎች ይገልፃሉ፡፡ የደምና የአጥንት ውስጥ ካንሰር የሆነው ሉኪሚያ ደግሞ በኢትዮጵያ የህፃናቱ ዋናው የጤና እክል ነው፡፡

በመሆኑም በዚህ በሽታ ተይዘው የሚመጡ የህፃናት ቁጥር መጨመሩን ነው የተነገረው፡፡ ዶ/ሮች እንደሚሉት ‹‹ወላጆች በህፃናት አመጋገብ ላይ ትኩረት እስካላደረጉ ድረስ በአሳሳቢነቱ መቀጠሉ አይቀርም፡፡ ወላጆች ለልጆቻቸው ትኩስና አዳዲስ የሆኑ ምግቦችን ከመመገብ ይልቅ፣ የታሸጉ መጠጦችንና ምግቦችን ማስለመዳቸው ለካንሰር መስፋፋት ዋነኛው ምክንያት እንደሆነ ነው የተገለፀው፡፡

በህይወት ዘመናቸው ከሶስት ሴቶች አንዷና ከአምስት ወንዶች አንዱ በካንሰር የመያዝ ዕድል እንዳላቸው አለምአቀፍ ጥናቶች ያመለክታሉ፡፡ ከዚህ አንጻር ወንዶችን በብዛት የሚያጠቁና ወዲያው ቢታወቁ ለመክሰም የሚችሉ የካንሰር አይነቶችን እንዲመረመሩ ይመክራል፡፡ በተለይም ወንዶች ከ50 ዓመት በኋላ፣ ሴቶች ከ35 ዓት ዕድሜ በኋላ የካንሰር ቅድመ ምርመራ እንዲያደርጉ ይመከራል፡፡ ወንዶችን በተመለከተ የሳንባ ካንሰር፣ የትልቁ አንጀት ካንሰርና ፕሮስቴት ካንሰር ዋና ዋናዎቹ ሲሆኑ፣ ሴቶችን በተመለከተ ደግሞ የጡት ካንሰር፣ የማህፀን በር ካንሰር፣ የሳንባ ካንሰር፣ የትልቁ አንጀት ካንሰር፣ የማህፀን ጋን ካንሰር፣ የዕንቁላል ዕጢ (ኢቫሪያን) ካንሰርና የቆዳ ካንሰር ተጠቃሽ ናቸው፡፡
 

Hiber Radio: ደቡብ ሱዳን ለከበባ ገባሁ ያለው የኢትዮጵያ ጦር በግዛቴ ውስጥ የለም አለች |በአራቱ የኦሮሞ ድርጅቶች በጋራ ለመታገል መወሰን ዙሪያ ቃለምልልስ ከአቶ አሚን ጁዲ ጋር

0
0

ጋዜጠኛ ሃብታሙ አሰፋ

ጋዜጠኛ ሃብታሙ አሰፋ


የህብር ሬዲዮ ሚያዚያ 30 ቀን 2008 ፕሮግራም

እንኳን ለእናቶች ቀን አደረሳቹ!

አራት ለኦሮሞ ሕዝብ ነጻነት የሚታገሉ ተቃዋሚ ድርጅቶች በቅርቡ በሚኒሶታ ላይ ባደረጉት ስምምነት በጋራ ለመታገል ወስነዋል። የኦሮሞ ነጻነት ግንባር፣ የኦሮሞ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ፣የተባበረው የኦሮሞ ነጻነት ግንባርና የኦሮሚያ ነጻ አውጭ ግንባር ናቸው። አቶ አሚን ጁዲ ድርጅቶቹ በጋራ ለመታገል ባደረጉት ስብሰባ ላይ ድርጅታቸውን በመወከል ተገኝተዋል። ስለ ትብብሩ ከአቶ አሚን ጁዲ እና ከጋዜጠኛ በፍቃዱ ሞረዳ ጋር ተወያይተናል። (ሙሉውን አድምጡት)

<...>

የቀለም ቀንድ ጋዜጣ ስራ አስኪያጅ ጋዜጠኛ አበበ ውቤ ክትትልማ ማስፈራራት እየተደረገበት መሆኑን ገልጾ ለህብር ከሰጠው ቃለ መጠይቅ የተወሰደ(ሙሉውን ያዳምጡት)

በካናዳ አልበርት ግዛት የተከሰተውን የሰደድ እሳት አደጋና በዚያ የሚገኙ ኢትዮጵያውያንን አስመልክቶ የከተማው ነዋሪ ከሆነው ጋዜጠኛ ሰይፉ መኮንን ጋር ያደረግነው ቆይታ (ሙሉውን አድምጡት)

የአፍሪካ አምባገነኖች የስልጣን ሙጢኝ በሽታን ኮፊ አናን በቅርቡ በኢትዮጵያ ተገኝተው ያወገዙበት ስብሳባ ሲቃኝ (ልዩ ጥንቅር)

በቬጋስ የሕወሃት አገዛዝ የጠራው ስብሰባ ስለደረሰበት ተቃውሞ ቃለ መጠይቅ

በአዲስ አበባ ቤታቸው ያለማስጠንቀቂያ የፈረሰባቸው ነዋሪዎች አሉበትን ሁኔታ በተመለከተ ከአካባቢው ያደረግነው ቃለ መጠይቅ ይዘናል

ሌሎችም

ዜናዎቻችን

ደቡብ ሱዳን ለከበባ ገባሁ ያለው የኢትዮጵያ ጦር በግዛቴ ውስጥ የለም አለች

የቀለም ቀንድ ጋዜጣ ስራ አስኪያጅ የጸጥታ ሀይሎች ሊገድሉት መዛታቸውንና ክትትል እየተደረገበት መሆኑን ገለጸ

ኦብነግ ኢትዮጵያ እየታመሰች ነው ይላል

ዓለም አቀፉ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅት የቀድሞው የሰማያዊ ፓርቲ የሕዝብ ግንኙነት ሀላፊ ዮናታን ተስፋዬ ያለ ቅድመ ሁኔታ እንዲፈታ ጠየቀ

በአዲስ አበባ ሕገ ወጥ ጥቅም ጠይቀው ያልተሳካላቸው ባለስልጣናት ያለ ማስጠንቀቂያ ሕገ ወጥ ያሏቸውን ከሰማኒያ በላይ ቤቶች አፈረሱ

በቬጋስ የሕወሃት አገዛዝ በብአዴን ስም የጠራው ስብሰባ ጠንካራ ተቃውሞ ገጠመው

የኤርትራ መንግስት ደጋፊዎችና ተቃዋሚዎች እስራኤል ውስጥ ተጋጩ

የቢን ላዲንን ዱካ ለአሜሪካኖች የጠቆሙት ዶ/ር በእስር ቤት እየማቀቁ ነው

አሜሪካኖችና የሰብአዊ መብቶች መከበር ጥያቄ በኢትዮጵያ አክሎግ ቢራራ (ዶ/ር)

0
0

Dr Aklog Birara
ኢትዮጵያን በሚመለከት በዚህ ወር በአሜሪካ ምክር ቤት ሁለት ያልታሰቡ ውይይቶች ተካሂደዋል፤ አንድ የአቋም ሰነድ ይፋ ሆኗል። የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት ከአርባ ገጽ በላይ የሚሆን በመረጃ የተደገፈ ሰነድ ይፋ አድርጓል። የሰብአዊ መብቶች አለመከበር ለኢትዮጵያና ለአካባቢው ሰላም፤ እርጋታና አብሮ መኖር አደገኛ፤ ለአገሪቱ ዘላቂና ፍትሃዊ እድገት እንቅስቃሴ ማነቆ መሆኑን ጠቅሶ የኢትዮጵያ መንግሥት የኢትዮጵያዊያንን ነጻነት፤ ክብር፤ ህይወት፤ ሰብአዊ መብትና
ደህንነት እንዲያከር ጠይቋል። በተመሳሳይ፤ አንድ የአሜሪካ ምክር ቤት ክፍል በኦሮሞያ የተካሄደውን ግድያና ሌላ ተመልክቶ የባለሞያዎች ዘገባ አድርጓል። የተገኙት ባለሞያዎች የኦክላንድ ኢንስቲቱት መስራችና ዲሬክተር፤ የአልጀዚራና የአምነስቲ ኢንተርናሽናል ጋዜጠኞች ነበሩ። በዚህ ውይይት ብዙ መቶ የሚሆኑ የኦሮሞያ ብሄር ተወካዮችና ሌሎች ኢትዮጵያዊያን በተመልካችነት ተገኝተዋል። ውይይቱ ወደ ምክር ቤቱ መደበኛ ዘገባና አቋም ያመራል የሚሉ ተመልካቾች አሉ። ይህ ሊሆን ወይንም ላይሆን ይችላል። የአሜሪካኖቹ ትኩረት አዲስ ፕሬዝደንት ከመምረጡ ላይ ስለሚሆን በምክር ቤት ደረጃ ሌላ አቋም ይወሰዳል የሚል ግምት የለኝም።

Read Full Story in PDF

Viewing all 15006 articles
Browse latest View live