Quantcast
Channel: Ethiopian News | ዘ-ሐበሻ | Latest News Provider | News For All
Viewing all 15006 articles
Browse latest View live

ገንዘቤ ዲባባ ዛሬ በፖርትላንድ ኦሪገን ያሸነፈችበትን ቪዲዮ ይመልከቱ | Video


ሠላምን ጀግኖች ከፈሪዎች ይልቅ ይፈልጓታል –ሰርፀ ደስታ

$
0
0

peace-dove1ጀግኖች ጦርነትን አይፈሩም እንጂ ጦርነትን አይወዱም፡፡ ሠላም ባይኖር ጦርነቱን የሚጋፈጡት ጀግኖች ናቸው፡፡ በተቃራኒው ፈሪዎች ጦርነትን መጋፈጥ ይፈራሉ እንጂ  ሠላምን አይፈልጓትም፡፡ የእነሱ ኑሮ ሁል ጊዜ በግርግር ውስጥ ተደብቆ ጀግና መሆንን ነውና፡፡ ይሄ ሰዎች ባለፉበት ታሪክ ውስጥ ሁሉ ያለ እውነታ ነው፡፡ ሰሞኑን አንድ በአንድ አስተያየት ሰጭ የፕሮፌሰር ኤፍሬም ይሳቅን በስልጣን ላይ ባሉትና ተቃዋሚ በሚባሉ ድርጅቶች መካከል ድርድር እንዲደረግ የሚያደርጉትን የሽምግልና ሂደት በመተቸት የወጣው ጽሑፍ ከአለማወቅ ከሆነ እሺ ግን እኔን አልተመቸኝም፡፡ ኤፍሬም የሳቅ ከማንም በላይ ለዚያች አገር ሠላም መሆን የሚያስቡና ጥረታቸው ሁሉ የትክክለኛ ኢትዮጵያዊ እንደሆነ ነው እኔ የምረዳው፡፡ በተግባርም ቢሆን ከማንም በላይ ኢትዮጵያዊነትን ለአለም ሳይቀር አግዝፈው የሚያሳዩ ናቸው እንጂ በኢትዮጵያ ጉዳይ ከእሳቸው እሻላለሁ ብሎ ሊታቻቸው የሚችል ያለ አይመስለኝም፡፡ ጸሐፊው አሁን የተፈጠረውን አጋጣሚ ተጠቅሞ ለኢትዮጵያ ሠላም የሚሠሩትን ኤፍሬምን በሕዝብ ዘንድ እንዳይታመኑ ለማድረግ የሚሞክር ነው የመሰለኝ፡፡ ኤፍሬም ይሳቅ እኮ መሰሉኝ የ1997ዓ.ም ምርጫ ተከትሎ ለእስር የተዳረጉ ወገኖችን በእርቅ እንዲፈቱ ያደረጉት፡፡ እንደ እሳቸው ምኞትማ ከዛም በላይ ነበር፡፡ ብሔራዊ መግባባት እንዲኖር የራስን ችግር ሕዝቡ በሚረዳውና ኢትዮጵያዊ በሆነ ባሕልና ወግ የፖለቲካ ድርጅቶች እርስ በእርስ በጠላትነት የሚተያዩበትን መንፈስ አስወግደው በመግባባትና በትክክለም እውነተኛ በሆነ ለአገርና ሕዝብ መሠረት በሚሆኑ ጉዳዮች ተቀራርበው እንድሰሩ ብዙ ሞክረዋል፡፡ እስካሁንም ሲሞክሩ ነበር፡፡ በተቃራኒው እንደዚሁ እንዳሁኑ የወያኔ አጋር በሚል ጥረታቸው እንዳይሰምር ብዙዎች ያጥላሉባቸዋል እንጂ፡፡

ኤፍሬም ይሳቅ የሟቹ የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒሰቴር ወዳጅ እንደነበሩ ይታወቃል፡፡ ይህ ማለት ኤፍሬም የተቃዋሚ ድርጅቶች ጠላት ናቸው ማለት አልነበረም፡፡ ይሄንን መለስም አሳምረው ያወቁት ነበር፡፡ ኤፍሬም ከአሁን ባለስልጣኖች የሚያገኙት የተለየ ጥቅም አለ ብዬም አላምንም፡፡ ይልቁንም የኤፍሬም ጽኑ የሆነ የኢትዮጵያዊነትና  የኢትዮጵያን ጉዳይ በእኛው በራሳችን በባሕላችን በወጋችን በአመንበት በተስማማንበት እንጂ ማንም የማይመለከተው የፖለቲካና የኢኮኖሚ ጫና በማሳደር ሌላ አገሪቱ ለማትፈልገው ሥርዓት መዳረግ የለባትም የሚል እምነት ስላላቸው፣ ከቀድሞው ጠ/ሚኒሰቴር ጋር የነበራቸውን መቀራረብ ለእዚሁ ዓላማ ሊጠቀሙበት ሞክረዋል፡፡ በ1997ቱም ምርጫ የታሰሩ ወገኖቻችንን ለማሰፈታት ተጠቅመውበታል፡፡ ይሄው ሂደት በቀጣይ ሁሉንም የፖለቲካ ድርጅቶች ፉጹም ሠላማዊ በሆነ መልኩ እንዲሳተፉ ለማደረግ ቀጥለውም ሞክረውት ነበር፡፡ እንደተረዳሁት ከተቃዋሚ ተብዬዎች የተሰጣቸው ምላሽ ጥሩ አይመስለኝም፡፡ ኤፍሬም ማንንም ተቃዋሚ ድርጅት አግባብተው ከአላማው አላደናቀፉም፡፡ እሳቸው አላማቸው ተቃዋሚ እንዳይኖር ሳይሆን ተቃዋሚም ይሁን ገዥ ለኢትዮጵያና ሕዝቦቿ ጠቃሚ በሆነ ሠላማዊ በሆነ መልኩ አስተዋጽዖ እንዲኖራቸው ነው፡፡ ለኢሕአዴግ ባለስልጣናት ወዳጅ በመሆናቸው ኢሕዴግ እንደፈለገው በሕዝብ ላይ እንዲፈነጭ አይፈልጉም፡፡ ወዳጅነታቸው ሕዝብን ሲበድል ልክ አይደለም የምትሰሩት ለማለት እድሉን የፈጥርላቸዋል እሳቸውም ከግል ፍላጎት ያልሆነ ከልብ የሆነ በጎነት ነው፡፡

ይልቁንም እሳቸውን ሊተች የሞከረው ጸሐፊ ኢሕአዴግ አሁን አሁን ኦነግንና ግንቦት 7ን በጉዳያቸው ማየት ጀምረዋል እና የመሸነፍ አይነት ይመስላል በማለት የማዘናጋት መልዕክት እያስተላለፈ ይመስላል፡፡ ሲጀምር ኦነግ ከኢሕአዴግ ባለስልጣናት ጋር ሥዎር ግንኙነት እንዳለው እኔ ብቻ ሳልሆን ብዙ ኢትዮጵያውያን ያምናሉ፡፡ ብዙዎች ኦነግ በኢአዴግ ባለስልጣናት ተሸውዶ ትጥቅ እንደፈታ ይገምታሉ፡፡ ሂደቱ ግን የሆነው የሕዝብን ልጆች ለሞትና እንግልት ማግዶ ኦነግ በቦሌ በኩል በአውሮፕላን ነበር ባለስልጣኖቹ ወደሚመቻቸው አገር የተሸኙት፡፡ ከዚያም በኋላ የኦነግ ዋነኛ የተባሉት ኢትዮጵያ መጥተው እንደተመለሱ እናውቃለን፡፡ የሕዝብ ልጅ ግን በማያውቀው ሳይቀር ኦነግ የሚል ታርጋ እየተለጠፈለት ስንቱ ለመከራና ለሞት ተዳርጓል፡፡

ሌሎች ተቃዋሚዎችም ቢሆኑ አሁን ያሉትን ባለስልጣናት መጥላታቸው አይደለም መመዘኛቸው፡፡ አሁን ያለውን ሥርዓት ለውጦ ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ከኢትዮጵያ ምድር የሆዳም ባለስልጣናት መፈንጫነቷ ቀርቶ የዜጎች ሠላማዊና ምቹ መኖሪያ የምትሆን አገርን መገንባት ዓላማው በሆነ ሥርዓት መገንባት ማየትን ነው ሕዝብ የናፈቀው፡፡ ለዚህ ደግሞ በኃይል ሳይሆን በሠላማዊ መልክ የመጣ ለውጥ አስተማማኝነት ይኖረዋል፡፡ ስለሆነም በተገኘው አጋጣሚ ሁሉ በሠላማዊ መልክ ኢትዮጵያ የናፈቀችውን አስተዳደር ማሳካት ከሁሉም ቅድሚያ የሚሰጠው ነው፡፡ ፕሮፈሰሩ እያደረጉ ያሉት ይሄንኑ ይመስለኛል፡፡ እርስ በእርስ ስላለው የድብብቆሽ ጫወታ እሳቸው ሊቆጣጠሩት አይችሉም፡፡ ሁሉም አካላት በቁርጠኝነት ሊመጡና መግባባት ቢችሉ ነው እንጂ፡፡ እርስ በእርስ ያለውን ድብብቆሽ ራሳቸው ድርጅቶቹ በሚተዋወቁበት ተንኮል መከታተልና ላለመሸወድ መጠንቀቅ ነው፡፡ በእኔ እምነት ኤፍሬም ይሳቅ ሆን ብለው ለአንዱ በመወገን አንዱን በተንኮል ጠልፎ ለሌላው አሳልፎ ለመስጠት የሚያደርጉት ሴራ የለም፡፡ እስከሚገባኝ የሄ ለእሳቸው የሚመጥን አድራጎት አይደለም፡፡ ከእድሜያቸውም ለኢትዮጵያም ካላቸው በጎነትና ፍቅር ይሄ የእሳቸው አላማ እንዳልሆነ እረዳለሁ፡፡ ራስን በጨለምተኝነት ዘግቶ ሌላውን ገና ለገና ተንኮለኛ ነው ብሎ ከማሰብ በጥንቃቄና ትክክለኛ ስልት ነድፎ መቅረብ ተገቢ ነው፡፡ ሌላው ሰዎች በራሳቸው ድክመት የተሸነፉበትን ለሌላው ማሳበብ ይፈልጋሉ፡፡ ኤፍሬም ዋስትና መስጠት አይችሉም፡፡ እሳቸው የሚችሉት ማደራደርና ሁሉም ኢትዮጵያዊነትን አላማ ያደረገ መግባባት እንዲኖር እድል ማመቻቸት ነው፡፡ ከዚህ ውጭ አኝህ ሰው ድብቅ አላማ አላቸው ብሎ የሚያምን ካለ ይንገረንና እንወቀው፡፡ አሁን ያለው ችግር ሰዎች እንደልባቸው መጻፍ ስለቻሉ ብቻ መልካሙን ነገር አጠልሽቶ እርግማኑን ማግዘፍ ነው፡፡ ከሁሉም በላይ ጸሐፊው ኢሕአዴግ ፈርቷል አሁን አሁን ተቃዋሚዎችንም ድርጅት በክፉ ማንሳት እየተወ ነው በሚል የማዘናጊያ የሚመስል መልዕክት ነው ያስተላለፉልን የመሰለኝ፡፡ በተጨባጭ ያለው እውነታ ይሄ አይደለም፡፡ ጭራሽ ክልሎችን በወታደራው አስተዳደር ሥር እያስገበ እያየን አንሸወደም፡፡ ከዚህ በላይ ምን አለብኝነት የለም፡፡ ኦሮምያ የሚባለው ክልል እንደልቡ የሚዘውረው ክልል እንሆነም ታይቷል፡፡ አሁን በኦሮምያ የምናየው እንደ አማራ በሚባሉት አይነት ክልል የሚሞከር አይመስለኝም፡፡ ኦነግና ኢሕአዴግ የኦሮምኛ ተናጋሪውን ልጆች ከኢትዮጵያነቱ እንዲመክን የደረጉት የዘመናት ጥረታቸው ውጤት ነው፡፡ ትውልዱ በማንነቱ ስለባዘነና ብዙ ምሁር ነን የሚሉትም የጥላቻ ልክፍት የተመረዙ በመሆኑ ከዚህ የሚያሕል ክልልና ሕዝብ አንድ ጠንከር ያለ አቋም ያለው ሰው ጠፍቶ ማንም እንደልቡ የፈነጭበታል፡፡ ኦሕድድ ከሚባለውስ እንዴት አንድ ሰው እንኳን ይጠፋል; የኦሮሞ ምሁር ነን የሚሉትማ አብዛኞቹ አሁንም የሚያባንናቸው እነሱ ነፍጠኛ የሚሉት ያ አማራ የሚሉትና ሚኒሊክ ናቸው፡፡ ሚኒሊክ እኮ ከሞቱ መቶ ዓመት ሆናቸው፡፡ ሌሎች እኮ በ17 ዓመት ነው ዛሬ ስልጣን የየዙት፡፡ ኦነግ ተብዬው እኮ ሲፈልግ 70 ዓመት ታግያለሁ ባይ ነው፡፡ ዓላማው ሁሉ ሌላውን ከመጥላት ጋር የተያያዘ መሆኑ ነው እንጂ የሄን ያህል ሕዝብ ደጋፊ እያለው በ7 ወር ስልጣን በያዘ ነበር፡፡ ቢሳካለት ግን ምን ሊሆን ነበር; ኤፍሬም ሙከራቸው እንዲህ ያለ እርግማን የሆነ አስተሳሰብ ከኢትዮጵያ እንዲጠፋ ነው፡፡ ይህን አስተሳሰባችሁን ተው የሚለን ሰው አንፈልግም ከሆነ ደግሞ ችግሩ የኤፍሬም ሳይሆን የጠለሸ አስተሳሰብ ያላቸው ነው፡፡ ኦነግን እኮ ኤፍሬም ብዙ ጊዜ ሞከረውት ነበር፡፡ ኤፍሬምና ኦነግ ኢትዮጵያዊነት ላይ የሚግባቡ አይመስለኝም፡፡ ከዓለም አገራት ሁሉ ሳይቀር ኢትዮጵያን እንደ ልዩ ምድር የሚቆጥሩት ኤፍሬምና ኢትዮጵያ ከምድረገጽ እንድትጠፋ የሚፈልገው ኦነግ መግባባት አላስቻላቸውም፡፡

ይልቁንም ሠላም የሚፈልግ ሁሉ ኤፍሬም የተነሱበትን አላማ ቢደግፍ ለውጥ ይመጣል ባይ ነኝ፡፡ ተቃዋሚም ይሁን ገዥ ኤፍሬም የሚመኟትን ኢትዮጵያ ማሰብ ቢችል ወራት ያለፈጀ ለውጥ ይመጣል ባይ ነኝ፡፡ ችግሩ የኢሕአዴግ ባለስልጣናትም ገንዘብ፣ሆዳቸው፣ እርግማን አደንድኗቸዋል ተቃዋሚዎችም ጥላቻ፡፡ ኤፍሬምና አጋሮቻቸው ተሳክቶላቸው ማግባባት ቢችሉ በምን እድላችን፡፡ ለበጎ ነገር ጠላቶች አንሁን

እግዚአብሔር ኢትዮጵያን ይባርክ! አሜን!

The post ሠላምን ጀግኖች ከፈሪዎች ይልቅ ይፈልጓታል – ሰርፀ ደስታ appeared first on Zehabesha Amharic.

ፍቅራችን የት ገባ? –ከተማ ዋቅጅራ

$
0
0
ከተማ ዋቅጅራ

ከተማ ዋቅጅራ

በአሜሪካ አገር በተደረገው የአለም አትሌቲክስ ሻንፒዮና ኢትዮጵያ አመርቂ ድልን በልጆቿ ተቀናጅታለች። ጥቂት ተወዳዳሪ በማሰለፍ ብዙ መዳሊያን ከሚያገኙት አገራት ውስጥ ግንባር ቀደሙ እኛ ነን ብል የተሳሳትኩ አይመስለኝም። ከብዙ የውድድር ዘርፎች ውስጥ በጥቂቱ ብቻ በመሰለፍ ከአለም ተወዳዳሪ አገራት መካከል በመዳሊያ ብዛት ውስጥ በመግባት ኦሎምፒክም ሆነ የአለም ሻንፒዮናም ሆነ ክሮስ ካንትሪም ሆነ በአትሌቶቻችን ጥንካሬ እና በህዝባችን ጸሎት የደረጃ ሰንጠረዥ ውስጥ በመግባት ኢትዮጵያን ከ1-10 ውስጥ ትጨርሳለች።
ከአበበ ቢቂላ ብጀምር፡- አበበ የመጀመሪያው አፍሪካዊ የማራቶች አሸናፊ፣ የመጀሪያው አፍሪካዊ የኦሎምፒክ አሸናፊ እና የሪከርድ ባለቤት፣ የመጀመሪያው ብቻ ሳይሆን የመጨረሻም በሚያስብል መልኩ ሊደፈር የማይችል የማራቶንን ውድድር በባዶ እግሩ የሮጠ፣ የሮጠ ብቻም ሳይሆን ውድድሩን ያሸነፈ የአለማችን ብርቅዬ እና ብቸኛ አትሌት አበበ ቢቂላ ነው። አበበ ሁለት የኦሎምፒክን ማራቶን ውድድርን ካሸነፈ በኋላ ሶስተኛው ላይ በሆዱ በደረሰበት ህመም ምክንያት ውድድሩን ሲመራ ቆይቶ መያል ለይ ህመሙ እያየለበት ሲመጣ ያቅተዋል የዚህን ግዜ ውስጡ በሃዘን ተዋጠ የሱ አሸንፎ የመዳሊያ ባለቤት መሆኑ ሳይሆን የኢትዮጵያን ስም ዳግም ማስጠራቱ ባለመቻሉ ነበረ። ወደ ማሞ ወልዴ ተጠግቶ በል እንግዲህ እኔ በጣም አሞኛል ውድድሩን መጨረስ አልችልም የኢትዮጵያ ህዝብ አደራው አንተ ለይ ነው ያለው አሸንፈህ ባንድራችንን ከፍ አድርገህ ማውለብለብ አለብህ አለውና ወደኋላ ቀረ። ማሞ ወልዴም የአበበን አደራ ተቀብሎ በድል ማጠናቀቅ ችሏል።
ሲቀጥል በነ ዋሚ ቢራቱ፣ በነ ምሩጽ ይፍጠር፣ በነ ቶሎሳ ቆቱ፣ በነ መሐመድ ከድር፣ በነ ፍስሐ አበበ፣ በነ ፊጣ ባይሳ፤ በተወዳደሩበት ውድድሮች ላይ ተከታትለው በመግባት አረንጓደው ጎርፍ የሚል ስያሜ እስከማስገኘት ብርቅዬ አትሌቶችን ኢትዮጵያ አፍርታለች። በነዚህ አትሌቶች ዘመን 7 አትሌቶች የጎዳና ውድድር ላይ ለመወዳደር ወደ ውጪ ይሄዳሉ በዚህ ውድድር ፍስሐ አበበ ያሸንፍና 15ሺ ዶላር ይሸለማል ሌሎቹ ግን ምንም ሽልማት ሳያገኙ ይቀራሉ አትሌት ፍስሐ የተሸለመውን 15ሺ ዶላር ለሰባቱም እኩል ያካፍላል። ውጠቱ የኔ ብቻ አይደለም የናተም ጭምር ነው በማለት ብሩን ያካፍላቸዋል። በፍቅር ለሃገር ፍቅር የሚሮጡ ሲያሸንፉም በፍቅር የሚተቃቀፉ የተሸለሙትንም ሽልማት በፍቅር የሚካፈሉ አገራቸውንም ህዝባቸውንም የሚወዱ አትሌቶች ነበሩን።
በነ ደራርቱ ቱሉ፣ በነ ጌጤ ዋሚ፣ በነ ወርቅነሽ ኪዳኔ፣ ዘመን በኦሎምፒክ እና በአለም ሻንፒዮን ውድድር ላይ ኢትዮጵያኖቹ ኮኮቦች ደምቀው መታየት ብቻ ሳይሆን ከድል በኋላ በፍቅር ተቃቅፈው ባንድራ ለብሰው እየተሳሳሙ የሚላቀሱ ነበሩ።
በነ አሰፋ መዝገቡ፣ በነ ሐይሌ ገብረስላሴ፣ በነ ሐብቴ ጁፋር፣ ዘመን የኢትዮጵያ ኮኮቦች በአለም ሲደምቁ ከድል በኋላ ከአሸናፊው ጋር አብረው በመሆን የአንዱ ድል የሌላው ድል የአንዱ ማሸነፍ አገር እንዳሸነፈች በመቁጠር ደስታቸውን አብረው ባንድራ ለብሰው ይገልጹ ነበረ። ሲዲኒ ኦሎምፒክ ላይ ሃይሌ እና ፖል ቴርጋት ያደረጉት እልህ አስጨራሽ ውድድር አሰፋ መዝገቡ ሶስተኛ በመሆን ነበረ ያጠናቀቀው። አሰፋ ከራሱ እሩጫ ይልቅ የሃይሌን ማሸነፍ እየሮጠ ይጨነቅ ነበረ። ሃይሌም በድል ሲያጠናቅቅ የራሱን ትልቅ ድል እረስቶት ውድድር ውስጥ ሆኖ ሜዳ ላይ ደስታውን ይገልጽ ነበረ ፍቅር ማለት እንደዚ ነው። በወንድም ድል እንደራስ መደሰት የወንድም ድል የአገር ድል መሆኑን አውቆ የኢትዮጵያ አትሌት በድል ሲያጠናቅቅ በእውነተኛ ፍቅር ደስታን አብሮ መግለጽ ነው።
በነ ቀነኒሳ በቀለ፣ በነ ስለሺ ስህን፣ በነ ሃይሌ ገብረስላሴ በነ ኢማና መርጋ፣ በኦሎምፒክ እና በአለም ሻንፒዮና ስለሺ እና ቀነኒሳ ሃይሌ ወደኋላ በቀረ ግዜ አንገታቸውን እያዞሩ ይፈልጉ ነበረ ሌላው ቀርቶ ቀነኒሳ የውድድሩን ፍጥነቱን በመቀነስ ሃይሌ እንዲጠጋ ሙከራም አድርጎ ነበረ። በዚህ ውድድር ላይ ቀነኒሳ የወርቅ ስለሺ የብር ሃይሌ ደግሞ የአምስተኛን ደረጃ አግኝቶው አጠናቀዋል። በድሉም ሶስቱም ተቃቅፈው ደስታቸውን ሲገልጹ ነበረ ድል ብቻ ሳይሆን ፍቅርንም ያሳዩን ነበረ። ኢማና መርጋ በጣም ጠንካራ እና ጀግና አትሌት ብቻ ሳይሆን የፍቅር ሰውም ጭምር ነው። በየውድድሩ እዩት ለአገሩ ልጆች የሚያሳየው ከበሬታና ፍቅር ትልቅ ነው። ውጤቱን እሱም ያምጣው ማንም ኢትዮጵያዊ ካሸነፈ ከልብ የሚደሰት ልጅ ነው። ኢማና ፍቅርን እና የአገር የማሸነፍ ክብርን ካንተ ተምረናል።
ታዲያ ያሁኖቹ ምን ነካቸው? 90ሚሊዮን ህዝብን ወክለው መሮጣቸውን ለምን እረሱት? ጡርነሽ እና መሰረት በሚሮጡበት ግዜ ከራሳሸው ክብር ይልቅ ኢትዮጵያ አገራቸው ወክለው መሄዳቸውን እና 90 ሚሊዮን ህዝብን የማሸነፋቸውን ውጠት በጉጉት እንደሚጠብቅ አያውቁ ይሆንን? የአንዱ ማሸነፍ ሌላኛውን ለምን አያስደስታቸውም። ለኢትዮጵያ ህዝብ አገርን ወክለው እስከሄዱ ድረስ ሁሉም ለኛ አንድ ናቸው። ደስታችን ሙሉ እንዲሆን ለምድነው ፍቅርን ያላሳያችሁን? ውድድሩ እኮ የሁለት ወይንም የሶስት ሰዎች አይደለም የአገር ውድድር ነው። ኢትዮጵያ ደግሞ እናተን ልካለች። ታዲያ የአለማችን አገራት ሁሉ በመቅደም የኢትዮጵያን ባንድራ ከፍ የሚያደርጉ አትሌቶች ሁሉ ከራሳቸው ክብር የሃገር እና የህዝብ ክብር እንዴት ማስበለጥ አቃታቸው? ይሄንን ጽሁፍ ልጽፍ የቻልኩበት ምክንያት ዛሬ በገንዘቤ እና በመሰረት ውጤት ደስ ብንሰኝም ፍቅራችሁን ማየት ባለመቻላችን ግን ቅር መሰኘታችንን ሳልገልጽ አላልፍም ብዬ ነው።
በ3ሺ ሜትር ውድድር ላይ መሰረት እና ገንዘቤ የአመቱን ጠንካራ ውድድር እንደሚያደርጉ ሚዲያዎች ዘግበው ነበረ። መሰረት ከብዙ እረፍት በኋላ ወደ ውድድር መምጣቷ እንደሚከብዳት ቢታወቅም ባላት ልምድ ተጠቅማ ውጤታማ ትሆናለች የሚል ግምት የብዙሃሉ ግምት ነበረ። ገንዜቤ ደግሞ ከባለፈው አመት ጀምሮ ብቃቷን ለአለም ህብረተሰብ እያሳየች ያለች የባለ ብዙ ሪከርድ ባሌቤቶች ብቻ ሳትሆን ለ25 ዓመት ማንም ሊሰብረው ያልቻለውን ሪከርድ ጭምር በመስበር ብቃቷን ያሳየች በመሆኗ ከፍተኛ ግምት ተሰጥቷት ነበረ። በውድድሩም እንደተመለከትነው ገንዘቤ ከጥሩ ብቃት ጋር የአንደኝነትን ደረጃ ስትይዝ መሰረት የሁለተኝነትን ደረጃ ይዛ ውድድራቸውን በድል ጨርሰዋል። ሁለቱም የኢትዮጵያ ኩራት ልጆች ናቸው። ሁለቱም ለአገራቸው መዳሊያ በማስገኘት ባንድራችንን ከፍ አድርገው አውለብልበዋል። ታዲያ ገንዘቤ እና መሰረት ፍቅራችሁን ግን አላየንም። ፍቅራችሁን የት ወሰዳችሁት? መዋደዳችሁን የት ጣላችሁት? የኢትዮጵያ ህዝብ እኮ ከውጤታችሁ እኩል በድላችሁ ተቃቅፋችሁ ስትደሰቱ ማየት ይፈልጋል። ኽረ ፍቅር ወዴት እየሄደ ነው? በዚሁ የአለም ሻንፒዮና ላይ የሁሉም ሃገሮች ሲያሸንፉ ተቃቅፈው ደስታቸውን አብረው ይገልጻሉ 800 ሜትር የአሜሪካ የወንድ ሯጮች አንደኛ እና ሶስተኛ ወጥተዋል። አንደኛ የወጣው ጥቁር ነው ሶስተኛ የወጣው ነጭ ነው ውድድሩን ሲጨርሱ ግን ሁለቱም ተቃቅፈው ደስታቸውን አሳይተውናል ምክንያቱም ሁለቱም ሃገርን ወክለው ስለመጡ የአንዱ ማሸነፍ ለሌላው ደስታ ነውና። ታዲያ የኛዎቹ ምን ነካችሁ? ኸረ እየተስተዋለ። ወደፊትስ ምን አይነት ነገር ሊታይ ይችል ይሆን? የአትሌቶች አሰልጣኝ ለአትሌቶቹ ፍቅርንና መዋደድን አስተምሯቸው። አትሌቲክስ ፌዴሬሽን አትሌቶቹ በሚያሳዩት ጥሩ ያልሆነ ነገር ገስጿቸው እንዲዋደዱ እንዲከባበሩ አድርጓቸው ማንም ያሸንፍ የሃገር እና የህዝብ ሃላፊነት ስላለባቹሁ የአንዱ ማሸነፍ የነሱም ድል እንደሆነ ንገሯቸው። እኔ ግን ባሳዩት ፍቅር አልባ ድርጊት አዝኛለው። በእግዚአብሔር ቃል ጽሁፌን ላብቃ እምነት ተስፋ ፍቅር እነዚህ ሶስቱ ጸንተው ይኖራሉ ፍቅር ግን ይበልጣል ከሁሉ። ወደ ቀድሞ ፍቅራችን እንመለስ።
ከተማ ዋቅጅራ
21.03.2016
Email- waqjirak@yahoo.com

The post ፍቅራችን የት ገባ? – ከተማ ዋቅጅራ appeared first on Zehabesha Amharic.

ሳቂታዋ የረጅም ርቀት ሩጫ ንግስት ደራርቱ ቱሉ

$
0
0

Derartu Tulu

ዛሬ የደራርቱ ቱሉ ልደት ነው:: ይህችን ታላቅ ጀግና በቁም እያለች ማክበርና ማመስገን ሌሎችን ማበረታትም ጭምር ነው:: የደራርቱን ልደት በማስመልከት ተወዳጁ የስፖርት ጋዜጠኛ ፍሰሃ ተገኝ በቶታል 433 ድረገጹ ከዚህ ቀደም ያስነበበንን ጽሁፍ ለግንዛቤ ይረዳ ዘንድ እንደወረደ አቅርበናል::

መልካም ልደት ለደራርቱ! መልካም ንባብ ለእርስዎ

ኦሎምፒክ ምን እንደሆነ ከማወቄ በፊት የእሷን ስምና ድሏን ነበር የማውቀው። ስሟ በሬዲዮ በተደጋጋሚ ሲጠራ ስለሰማሁት አእምሮዬ ውስጥ ተቀርጾ ተቀምጧል። “የኦሎምፒክ ወርቅ ሜዳሊያ ባለቤት ሆነች” የሚለው ጩኸት ልቤን አልሰረቀውም፤ ልጅ ነበርኩና የኦሎምፒክን ዋጋና ምንነት ባለማወቄ። “ሮጣ ተፎካካሪዎቿን እንደ ጭራ ከኋላ አስከትላ አሸነፈች” የሚለው ድምጽን ለማስተናገድ ግን አልተቸገርኩም። ምክንያቱም እየተሯሯጠና አቧራ እያቦነነ ለነበረ ልጅ ሩጫ፣ መቅደምና መቀደም ምን እንደሆኑ ለይቶ ለማወቅ አያስቸግረውምና።

ምን አልባት በተደጋጋሚ ፊቷ ላይ የሚታየው ፈገግታ ደራርቱ ቱሉን በተፎካካሪዎቿና ፊት-ለፊት የሚያየውን ነገር ብቻ ማንበብ በለመደ ሰው አይን ውስጥ ጠንካራና ቆፍጣና ተወዳዳሪ ላያስመስላት ይችላል። ተራራማዋ በቆጂ ውስጥ የተወለደችው ደራርቱ ግን ልክ የውድድር ማስጀመሪያው ሽጉጥ እንደተተኮሰ ነብር ትሆንና በአስደናቂ ብልሀት፣ በጽናት እና በጠንካራ ልምምድ ከታጀበው ውብ አሯሯጧ ጋር ተፎካካሪዎቿን እንዳልነበሩ አድርጋ የማሸነፍ ብቃት ያላት ድንቅ አትሌት ነች። ይሄንን ለማረጋገጥ የፈለገ ወደኋላ ብዙ መመለስ አያስፈልገውም። በህዳር ወር መጀመሪያ 2009 ዓ.ም የተካሄደው የኒው ዮርክ ማራቶን ለተወዳዳሪዎችና ሩጫውን ለመከታተል በከተማዋ ጎዳናዎች ላይ ለተገኘው ተመልካች የአየሩ ሁኔታ እጅግ በጣም ቀዝቃዛ በመሆኑ “ምን አለበት ከሞቀው ቤቴ ባልወጣሁ” የሚያሰኝ የነበረ ቢሆንም፤ ደራርቱ ታስብ የነበረው ግን ከድል በኋላ በደስታ ልታገኘው ስለምትችለው ውስጣዊ ሙቀት ነበር።

“ውድድሩ ሲጀመር አየሩ በጣም ቀዝቃዛ ነበር። እንዲያውም የሆነ ቦታ ላይ ለመውደቅም ተቃርቤ ነበር። ምስጋና ተጨማሪ ብርታት ለሰጠኝ እግዚአብሄር ይግባና ያንን አለፍኩ። ውድድሩን ከጨረስኩ በኋላ የተሰማኝ ግን ፍጹም ሌላ አይነት ስሜት ነው፤ በድል አድራጊነት የተገኘ የደስታ ሙቀት” አለች ተፎካካሪዎቿ የነበሩት ራሺያዊቷ ፔትሮቫን እና ፈረንሳዊቷ ዳውኔን  ቀድማ ውድድሩን በአሸናፊነት ያጠናቀቀችው ደራርቱ ለረኒንግ ታይምስ መጽሄት በጊዜው በሰጠችው አስተያየት።

derartu

እንዲህ ነች ደራርቱ፤ ፈተናዎቿን በፈገግታ በታጀበው የአሸናፊነት ስሜትና ድል ማሳለፍ የለመደች። ደራርቱን በጊዜው ማንም የኒዮርኩ ማራቶን አሸናፊ ትሆናለች ብሎ አልገመታትም። ምክንያቱም በ2006 ዓ.ም ልጅ ወልዳ ስለነበር ከሁለት አመታት በላይ ከሩጫው ከመራቋ በተጨማሪ፤ ውድድሮች ባደረገችባቸው ጥቂት ጊዜያት ውስጥም ጠንካራ የሚባልና ድሮ የስፖርቱን አፍቃሪ ያስለመደችውን አይነት አቋም ባለማሳየቷ ነው። ያደገችበት ባህል ልጅ ከወለዱ በኋላ ወደስራ በቶሎ መመለስን የማይደግፍ በመሆኑ በቶሎ ወደልምምድ ባለመመለሷ ምክንያት በአንድ ውቅት ክብደቷ በአብዛኛው ስትሮጥ ከነበራት 40ዎቹ አጋማሽ ኪሎ ግራም ላይ 18 ኪሎዎች ጨምራ ነበር። ከውድድር መራቅን፣ በወቅቱ የነበረው የኒው ዮርክን ቅዝቃዜ እና በርቀቱ የአለም የማራቶን ክብረወሰንን የያዘችውና ውድድሩን ታሸንፋለች ተብላ ትልቅ ግምት ተሰጥቷት የነበረችው ብሪታኒያዊቷ ፓውላ ራድክሊፍን የመሰሉ ጠንካራ ተፎካካሪዎቿና አስቸጋሪ ፈተናዎችን ከኋላ አስቀርታ ደራርቱ ቱሉ የኒው ዮርክ ማራቶንን ለማሸነፍ የቻለች የመጀመሪያዋ ሴት ኢትዮጵያዊ አትሌት ሆነች።

“በርግጥ አሸንፋለሁ ብዬ አልጠበኩም። ነገር ግን ጠንካራ ተፎካካሪ እንደምሆን አልተጠራጠርኩም። እስከመጨረሻው ለመታገል ቆረጥኩና ከእግዚአብሄር እርዳታ ጋር ለማሸነፍ በቃሁ። ባለፉት ሶስት አመታት ውስጥ ያሳለፍኩትን ሳስበው አሁን ያገኘሁት ድል የበለጠ እንድደሰት አድርጎኛል” አለች ደራርቱ ከድሉ በኋላ በፈገግታ በታጀበው አንደበቷ በሰጠችው አስተያየት።

በትምህርት ቤቷ በመካከለኛ ርቀቶች ተወዳድራ በተደጋጋሚ በአሸናፊነት ካጠናቀቀች በኋላ፤ እ.አ.አ በ1988 ዓ.ም አርሲን ወክላ በብሄራዊ አትሌቲክስ ሻምፒዮና ላይ በ1500 ሜትር ርቀት የነሀስ ሜዳሊያ ያገኘችው ደራርቱ፤ በአለም አቀፍ የሩጫ መድረኮች ላይ መታየት የጀመረችው በሀገር አቋራጭ ውድድሮች ላይ ነበር። ገና የ16 አመት ታዳጊ ወጣት እያለች እ.አ.አ በ1989 ዓ.ም የኖርዌዋ ስታቬንጋር ከተማ ውስጥ በተካሄደው  17ኛው የአለም አገር አቋራጭ ሻምፒዮና ላይ 23ኛ ደረጃን አግኝታ ጨረሰች። መሻሻልን እንጂ ወደታች መውረድን የማታውቀው ደራርቱ ምንም እንኳን የሜዳሊያ ፖዲዬም ላይ የሚያወጣት ውጤት ባታገኝም ከአንድ አመት በኋላ በተካሄደው የአለም አገር አቁራጭ ሻምፒዮና ከአለፈው አሻሽላ ውድድሩን 18ኛ ደረጃን አግኝታ አጠናቀቀች።

የመጀመሪያ አለማቀፋዊ ድልን ያገኘችው ግን በሀገር አቋራጭ ውድድር አልነበረም። በትራክ ወይም መም ውድድር እንጂ። እ.አ.አ በ1990 ዓ.ም በቡልጋሪያዋ ፕሎቭዲቭ ከተማ በተካሄደው በታዳጊ ወጣቶች የአለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና በ10 ሺህ ሜትር የተካፈለችው ደራርቱ አንደኛ ወጥታ የመጀመሪያ የሆናትን አለም አቀፋዊ የወርቅ ሜዳሊያ አገኘች። ማሸነፏ ሳይሆን ርቀቱን ለማጥናቀቅ የወሰደባት 32 ደቂቃ ከ56.26 ሰከንድ ነበር በጊዜው በሩጫው አለም መነጋገሪያ የሆነው። ወጣቷ ለውደፊት ትልቅ ተስፋ እንዳላት የገመቱ የዘርፉ ባለሞያዎች ጥልቅ ክትትል እያረጉባት እያለና በተለያዩ ብዙሃን መገናኛዋች ተስፋዋን እያስተጋቡ እንዳለ፤ በ1991 ዓ.ም ቶክዮ ጃፓን ውስጥ በተካሄደው የአለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና በግማሽ ፍጻሜው 10 ሺህ ሜትሩን 31 ደቂቃ ከ45.95 ሰከንድ በሆነ ጊዜ አጠናቃ በርቀቱ የኢትዮጵያን ክብረወሰን ሰበረችና የአለም የሴቶች ረጅም ርቀት ሩጫ ትኩረት ወደእሷ እንዲዞር አደረገች።

እ.አ.አ 1992 ዓ.ም በደራርቱ የአትሌቲክስ ህይወት ታሪክ ውስጥ ምን አልባት እጅግ በጣም ታላቁ እንደነበረ የሚነገርለት ነው። በዛ አመት በሶስት የ10 ሺህ ሜትር ውድድሮች ላይ ተካፍላ ሁሉንም ስታሸንፍ፤ ከባርሴሎናው ኦሎምፒክ መጀመር ጥቂት ቀደም ብሎ በተካሄደው የአፍርካ አትሌቲክስ ሻምፒዮና ላይ ርቀቱን በጊዜው የአህጉሪቷን ክብረወሰን በሰበረ 31 ደቂቃ ከ22.25 ሰከንድ ጊዜ አጠናቃ አንደኛ በመውጣት የወርቅ ሜዳሊያ አገኘች።

tulu

በባርሴሎናው ኦሎምፒክ የተፈጠረውን አለም የማይረሳው ነው። “ባርሴሎና ላይ ስካፈል ኦሎምፒክ ምን እንደሆነ ስለማላውቅ ልክ እንደማንኛውም አይነት ውድድር ነበር ያየሁት” ያለችውና በጊዜ 42 ኪሎ ግራም ክብደትና 1.56 ሜትር ቁመት የነበራት ደራርቱ፤ በታላቁ ኦሎምፒክ ጨዋታዎች ታሪክ አስደናቂ የፍጻሜ ውድድሮች ከሆኑት ተርታ የተመዘገበ እንደሆነ በተነገረለት የ10 ሺህ ሜትር ውድድር ልክ የማብቂያው 25ኛ ዙር ደውል ድምጽ ሲሰማ ውድድሩን ትመራ የነበረችው ደቡብ አፍሪካዊቷ ኤሌና ሜዬርን ቀድማ አፈትልካ ወጣችና የመጨረሻውን ዙር (400 ሜትር) በ64 ሰከንዶች በመጨረስ ሜዬርን በ30 ሜትሮች ያህል ቀድማ አንደኛ በመውጣት በኦሎምፒክ ታሪክ የወርቅ ሜዳሊያ ያገኘች የመጀመሪያዋ ጥቁር አፍሪካዊት ሴት ሆነች። አስደናቂ የነበረው ታዲያ ውድድሩን ያሸነፈችበት አጨራረስ ብቃቷ ብቻ አልነበረም፤ ስፖርታዊ ጨዋነቷም እንጂ። አሸናፊነቷን ያረጋገጠችው ደራርቱ ነጯ ደቡብ አፍሪካዊት ኤሌና ሜዬር ሩጫዋን እስክትጨርስ ቆማ ከጠበቀች በኋላ አቅፋት የእንኳን ደስ አለሽ መልእክቷን ማስተላለፏ ድንቅና በኦሎምፒኩ ከማይረሱት ምስሎች መካከል አንዱ ነበር። ከዚህ በኋላ ሁለቱ አትሌቶች የየሀገሮቻቸውን ሰንደቅ ዓላማ አብረው ጎን ለጎን በመሆን እያውለበለቡ የትራኩን ዙሪያ በመሮጥ ለተመልካቹ ድጋፍ ምስጋና ሲያቀርቡ ያየ በሙሉ “ምን አልባት የአድሲቷ አፍሪካ የወደፊት ታሪክ ብርሀናማ ሊሆን ይችላል” ብሎ እንዲያስብ ስድርጓል።

“ኤሌና በእንግሊዘኛ ስታዋራኝ ትዝ ይለኛል” አለች ደራርቱ ሁኔታውን ወደኋላ መለስ ብላ በማስታወስ። “ምንም እንኳን ምን እየነገረችኝ እንደሆነ ባይገባኝም [ፈገግታ] በምልክት መነጋገር ከጀመርን በኋላ በመግባባታችን ለረጅም ጊዜ ጓደኛሞች እንደሆነን አለን።”

የደራርቱን ስፖርታዊ ጨዋነት በርካታ እሷን የሚያውቋትና የአትሌቲክስ ስፖርት ባለሞያዎች “ፉክክር በበዛበት የስፖርት አለም ለማግኘት የሚከብድ ታላቅ ተምሳሌት” በማለት ይገልጹታል። በ2009 ዓ.ም በተካሄደው የኒው ዮርክ ማራቶን ተወዳዳሪዎቹ የርቀቱን ግማሽ ያህል ከሄዱ በኋላ ደራርቱ ቱሉና ፓውላ ራድክሊፍን ጨምሮ አምስት አትሌቶች ያሉበት የመሪዎቹ ቡድን ኩዊንስቦሮ ድልድይን እንዳቋረጠ ፓውላ ራድክሊፍ ህመም ይሰማትና ያንን ችላ እያቃሰተች ለመሮጥ ስትሞክር ያየችው ደራርቱ ዘውር ብላ “አይዞሽ በርቺ፤ ልንጨርስ ትንሽ ነው የቀረን” የሚል የብርታት መልእክትን ታስተላልፋለች። ሁለቱ አትሌቶች በሩጫው አለም የረጅም ጊዜ ታሪክ ያላቸው ቀንደኛ ተፎካካሪዎች መሆናቸውን የሚያውቁ ጋዜጠኞችና የስፖርቱ አፍቃሪ ባዩት ክስተት በጣም ነበር የተገረሙት። ታዲያ ውድድሩ ካለቀ በኋላ ሁኔታውን አስመልክቶ እንድታብራራ ከጋዜጠኞች ጥያቄ የቀረበላት ፓውላ “ደራርቱ ማለት ይቺ ነች፤ ከፉክክር ይልቅ መከባበርንና መዋደድን የምታስቀድም ጥሩ ሰው። ሌሎቹ ተፎካካሪ አትሌቶች ሲያልፉኝ እሷ ግን እንዳመመኝ ስላወቀች ጠጋ አለችና በኔ ፍጥነት ቀስ ብላ ከጎኔ እየሮጠች ‘አይዞሽ በርቺ’ አለችኝ” በማለት የደራርቱን ታላቅ ስፖርታዊ ጨዋነት ለአለም አስተጋባች።

በስፖርቱ አለም በርካታ አሸናፊዎች ቢኖሩም አስቸጋሪውና ፈታኙ ግን በድል አድራጊነት ለረጅም ጊዜ መቆየት ነው። ይሄንን ማድረግ የሚችሉ ደግሞ እንደ ደራርቱ ያሉ እጅግ በጣም ጥቂት ስፖርተኞች ናቸው። “ለተደጋጋሚ ጊዜያት መሮጥህ ልምድ እንዲኖርህና ከዛ እንድትማር ያደርግሀል። አገኘዋለሁ ብለህ ያሰብከው ቦታ ላይ ለመድረስ ደግሞ ጠንክረህ መስራት፣ በጽናትና በልበ-ሙሉነት መሮጥ አለብህ። በርግጥ እድሜህ በገፋ ቁጥር ጎልበትህና እግሮችህ ሊክዱህ ይችላሉ። ዋናው ትልቁ ችሎታ አእምሮህ ፈጣን እንደሆነ ማቆየቱ ላይ ነው” የምትለው ደራርቱ፤ የሩጫ ህይወቷ በጣም ረጅምና በድሎች ያሸበረቀ ነው። ይህ ድል እረጅም እድሜ ሊኖረው የቻለው በጠንካራ ስራ ምክንያት ነው። በ1996 ዓ.ም በተካሄደው የአትላንታ ኦሎምፒክ ሜዳሊያ ለማግኘት ያልተሳካላት ደራርቱ ቀጣዩ አላማዋ ከአራት አመታት በኋላ በሚካሄደው የሲድኒ ኦሎምፒክ ላይ ወርቅ ሜዳሊያ ማግኘት ነበር።

የደራርቱ በረጅም ርቀት ሩጫ ንግስትነትና መንፈሰ ጠንካራነት የፈረንጆቹ አዲሱ ሚሌኒዬም መጀመሪያ አመት ላይ በአውስትራሊያዋ ሲድኒ ከተማ በተካሄደው ኦሎምፒክ በደንብ የተረጋገጠበት ነበር። ከረጅም ጊዜ ጉዳት አገግማና የልጅ እናት ከሆነች በኋላ እንደገና ወደ ሩጫ ውድድር ተመልሳ አሸናፊ በመሆኗ “ምናልባት በቀዳሚነት ከማስቀምጣቸው ድሎቼ መሀል አንዱ ነው” ባለችው የሲድኒ ኦሎምፒክ የሴቶች 10 ሺህ ሜትር ሩጫ ውድድር፤ እስከመጨረሻው ዙር ድረስ ከመሪዎቹ ጋር አብራ ከሮጠች በኋላ ልክ የደውሉ ድምጽ ሲሰማ ከሀገሯ ልጅ ጌጤ ዋሚ፣ ከፖርቱጋላዊቷ ፈርናንዶ ሮቤሮ፣ ከብሪታኒያዊቷ ፓውላ ራድክሊፍ እና ከኬኒያዊቷ ቴግላ ላውሩፔ አፈትልካ የወጣችበት ታክቲክ ለእሷ የተለመደ፤ ለተመልካችና ለተፎካካሪዎቿ ግን እጅግ በጣም ድንቅ ክስተት ነበር። በአንድ ወቅት የውድድሮች ርቀት መጨረሻ ላይ ፍጥነት የመቀየር ችሎታዋን አስመልክታ ስትናገር “ውድድር ማብቂያ ላይ ከፊት ለፊቴ አስርም ሆኑ 20 አትሌቶች ቢኖሩ አልፌያቸው እንደምሄድ እተማመናለሁ” ያለችው ደራርቱ ቱሉ፤ የመጨረሻውን 400 ሜትር በ60.3 ሰከንዶች ዞራ መጨረሷ አስደናቂ የፍጥነት መቀየር ብቃቷን አሳይቷል።

የደራርቱን በሩጫው አለም ለረጅም ጊዜ ድል በድል መሆን በቅርበት ስትከታተል የነበረችውና በ1988ቱ የሶል ኦሎምፒክ በማራቶን የወርቅ ሜዳሊያ ባለቤት የሆነችው ሮዛ ሞታ፤ እ.አ.አ በሚያዚያ ወር 2001 ዓ.ም የለንደን ማራቶንን ካሸነፈች አራት ወራት ቆይታ በኋላ በካናዳዋ ኤድመንተን ከተማ በተካሄደው የአለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና በ10 ሺህ ሜትር አንደኛ ወጥታ የወርቅ ሜዳሊያ ባለቤት የሆነችው ደራርቱ ቱሉን አስመልክታ በጊዜው በሰጠችው አስተያየት “የምንጊዜም ታላቋ ሴት የረጅም ርቀት ሯጭ” በማለት መስክራላታለች። “ደራርቱ በሁሉም አይነት የሩጫ መድረክ ታላቅነቷን አሳይታለች። በትራክ፣ በጎዳናና በሀገር አቋራጭ ውድድሮች ከሷ የበለጠ ድልን ያገኘ አትሌት ማንም የለም። ለእኔ የምንጊዜም ታላቅ አትሌት ነች” አለች ሮዛ ሞታ።

ስለቀዳሚዋ የረጅም ሩጫ ንግስት ደራርቱ ቱሉ ታላቅነት ጽፎ መጨረስ አይቻልም። ምክንያቱም እሷ ለብዙዎች ከሯጭነት በላይ ነችና። በሲድኒ ኦሎምፒክ በማራቶን የወርቅ ሜዳሊያ ለኢትዮጵያ ያስገኘው ገዛኸኝ አበራ “አርአዬ የምትለው የስፖርት ሰው ማነው?” ተብሎ ሲጠየቅ “ያለምንም ጥርጥር ደራርቱ ቱሉ ነች” የሚል አጭርና ግልጽ ያለ መልስ ነበር የሰጠው።

እኔም በዚህ ላብቃ!

The post ሳቂታዋ የረጅም ርቀት ሩጫ ንግስት ደራርቱ ቱሉ appeared first on Zehabesha Amharic.

ዳቦ ለተራቡ ፣ መሬት ለጠገቡ! |ታሪኩ አባዳማ

$
0
0

ታሪኩ አባዳማ – መጋቢት 2008

“My village refused to move so they forced us with gunshots…”

Ethiopian farmer from Gambela region.

መሬት የዳቦ ምንጭ ነው። ሰማንያ በመቶ የሚሆነው ህዝብ በገጠር አራሽ የሆነባት ለሟ ኢትዮጵያ ዛሬ ሀያ ሚሊየን የሚደርሱ ዜጎቿ ዳቦ ለማኝ ናቸው። ገበሬ ሆኖ መሬት ከሌለው እሱ ብቻ ሳይሆን አገሪቱም ዳቦ የላትም – መሬትህን ከተቀማህ ትራባለህ – መሬትህን የቀማህ መንግስት ከሆነ ደግሞ በረሀብ እንድትሞት አስቀድሞ ፈርዶብሀል ማለት ነው።

Ogaden

ወያኔ መሬትህን ሲቀማ ቀጠሮ አይሰጥህም… ረሀብ ቀጠሮ እንደማይሰጥ ሁሉ…

መሬቱን ተነጥቆ በረሀብ አለንጋ የሚገረፍ ገበሬ በራሱ ቄዬ ከሚፈስ ጅረት ውሀ ቀድቶ እንዳይጠጣ አፉ የተለጎመ ፣ እጁ የተጠፈረ ፍጡር ያህል ነው… ‘የአባይን ልጅ ውሀ ጠማው…’ ሲል ይገልፀዋል ያገሬ ሰው። የዳቦ ምንጭ የሆነውን እርሻ መሬት በባለቤትነት መቆጣጠር አለመቆጣጠር የመሆን አለመሆን ፣ የመኖር አለመኖር ጥያቄ ነው። ከዚህም በላይ ባህል ፣ ቋንቋ ፣ ታሪክ ፣ ማንነት እና ስነልቡና… ከመሬት ይዞታ ጋር እጅግ የተቆራኘ ግንኙነት አላቸው። መሬት ዳቦ ብቻ ሳይሆን ማንነትም ነው።

ወያኔ በቀየሰው ኢኮኖሚ ረሀብ እና ድህነት ህዝባችንን እያመሰው ይገኛል። ይህ አነሰ ተብሎ ጥይት እና እስር ፣ አፈሳ እና ድብደባ… በገጠርም በከተማውም ህዝብ ላይ ሀያ አምስት ዓመታት ሳያባራ ጭራሽ እየባሰበት ቀጥሏል። ሃያ አምስት አመታት ስልጣን ላይ ተቀምጦ ረሀብን ማስታገስ ያልቻለ መንግስት በ2025 ወደ መካከለኛ ገቢ እርከን ከፍ ትላላችሁ እያለ ያላግጥብናል።

በሚሊየን ለሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን ዳቦ ከቶውንም ብርቅ በሆነበት በዚህ ዘመን በሚሊየን የሚለካ ለም መሬት ለጠገቡ ዘራፊዎች investors በወጉ ተለክቶ ሳይሆን ከዚህ ከዚያ ተራራ በመለስ በሚል የወፍ በረር ግምት ልቅ አግበስባሽነት (land grab) ሲሰጥ ቆይቷል። ከህንድ የመጣው ካሪቱሪ የተሰኘው መሬት አግበስባሽ ጋምቤላ 300ሺህ ሄክታር ለም መሬት በነፃ ተሰጠው ሲባል እውን የወያኔ ‘መሀንዲሶች’ በወጉ ለክተው የደረሱበት ስፋት ሆኖ አይደለም። ወያኔዎቹ ለዚህም የሚጨነቅ ህሊና ያላቸው ሰዎች አይደሉም።

ወያኔዎች የሚነድፏቸው የፖለቲካ ወይንም ኢኮኖሚ አቅጣጫዎች በአገር እና ህዝብ ላይ ለሚያስከትሉት አሉታዊ መዘዝ ቅንጣት ደንታ የላቸውም። ይህ ደግሞ ከጭፍን ድንቁርናቸው ብቻ ሳይሆን አለጠግብ ባይ ባህሪያቸው ብሎም ጠመንጃ ያሳበጠው እብሪታቸው ካስከተለው ዝርክርክት ጋር ተዳብሎ የመጣ ነው።

ላንድ ባለሀብት አንድ ግዙፍ የአገር አካል ቦድሰህ ስትሰጠው መሬቱ ላይ ያለውን ሰው ፣ እፅዋት ፣ ደን እና አራዊት እንዳሻህ አድርግ የሚል ሙሉ ስልጣን አስታቀፍከው ማለት ነው። ካሪቱሪ ያሻውን ያህል ደን ቢመነጥር ፣ ጫካ ቢያቃጥል ፣ አርሶ አደሮችን ቢያፈናቅል ወይንም የራሱን እስር ቤት አደራጅቶ አልፈናቀልም ፣ መሬቴን አለቅም ያሉ ዜጎችን ቢያጉርበት አንዳችም ተጠያቂነት እንደሌለበት ዋስትና እንዳለው ለማረጋገጥ ያህል 300ሺህ ሄክታር በፊርማ ፀድቆለታል። 100 ኪሎ ሜትር በ30 ኪሎ ሜትር ስፋት ያለው ትንሽ አገር ቢጤ ግዛት ተከልሎለታል ማለቱ ይቀላል።

ካሪቱሪ ከዚያ ማዶ ተራራ እስከ ወዲያኛው ማዶ ሸንተረር ጀርባ በተንጣለለው ማሳ ፣ ደን እና ቁጥቋጦ የ300ሺህ ሄክታር ባለቤት አድራጊ ፈላጭ ቆራጭ ያደረገውን የወያኔ ሰነድ እያሳየ ባሻው መንደር መሬት ገልባጭ ዶዘር ይዞ ገብቶ መዝጊያ እየገለበጠ ነዋሪውን ቢያፈናቅል ተጠያቂ አይደለም። እስከ ዛሬ ሲፈፅም እንደቆየው ሁሉ ደን ጨፍጭፎ ዛፍ ቸበችቧል ፣ እንኳን ሰው የዱር እንሰሳት ሳይቀሩ ተሰደዋል… ደግሞም የ300ሺ ሄክታር መሬት ካርታ ባለቤት መሆኑ ከኢትዮጵያ ባንኮች በሚሊየን የሚቆጠር ገንዘብ ለመበደር ብቁ አድርጎታል።… ድንቄም ባለሀብት… የተቀማ መሬት አስይዞ ከባንክ ብድር። አገሪቱ ምን ያህል በወሮበሎች እየተመዘበረች መሆኗን ይህ ብቻ በቂ ማሳያ ነው።

ለመሆኑ 300ሺህ ሄክታር ስፋቱ ምን ያህል ነው ብላችሁ ገምታችሁ ታውቃላችሁ? በግርድፉ ስንወስድ 3ሺህ ስኩዌር ኪሎ ሜትር ማለት ነው – አዲስ አበባ ስፋቷ 570 ስኬዌር ኪሎ ሜትር ነው። ለንፅፅር ይረዳ ዘንድ ጎረቤታችን ጂቡቲ አጠቃላይ ስፋቷ 23,200 ስኩዌር ኪሎ ሜትር ይሆናል።  ካሪቱሪ በወያኔ ስጦታ አዲስ አበባን 6 እጥፍ የሚበልጥ ፣ የጂቡቲን አንድ ሰባተኛ የሚያህል ለም መሬት እጁ አስገብቷል ማለት ነው። ካንድ አገር ትንሽ የሚያንስ ከትልቅ ከተማ ደግሞ እጅግ ሰፋ ያለ መሬት ማለት ነው።

ብትችሉ ጉግል አድርጉና ስሌቱን ድረሱበት – – አላሙዲ ጋምቤላ ላይ ብቻ 10ሺ ሄክታር መሬት ቀምቷል – 10 ኪሜ በ10 ኪሎ ሜትር ማለት ነው (100ኪሎሜትር ስኩዌር)። ቢኤችኦ 27 ሺሕ ሔክታር፣ ሩቺ 3,500 ሔክታር፣ ኬናን 10 ሺሕ ሔክታር፣ ኤስኤንድፒ 50 ሺሕ ሔክታር መሬት ያገኙት በጋምቤላና በቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልሎች ውስጥ ነው… በየ ክፍለ ሀገሩ የተንጣለለው የነ ሀጎስ እርሻ ሲታከል ስፋቱ የት እየለሌ ነው…

ቦብ ጌልዶፍ የተባለው ዝነኛ እንግሊዛዊ አቀንቃኝ ወያኔን በወታደራዊ ትጥቅ ለማጠናከር የሚረዳ 100 ሚሊየን የሚደርስ ዶላር የለገሰው ገና ጫካ ሳሉ እንደሆነ ሁላችሁም ታውቃላችሁ። ጌልዶፍ ውለታው መሬት አልወደቀም – ዛሬ እሱም ሰፊ የወይን እርሻ መሬት ባለቤት ሆኗል። 8 miles በሚል ስም የሚጠራው የጌልዶፍ ኩባንያ በመንግስት ይዞታ ስር የነበረውን አዋሽ ወይን ጠጅ ከነሰፊ ማሳው በቁጥጥሩ ስር አውሎ ‘እያለማ’ ነው። የወይን ጠጅ ምርታችንን በጥራትም በብዛትም ለማሳደግ ዘፋኙ ባለውለታ ሀላፊነት ተሰጥቶታል…

ይህን ሁሉ መሬት የተቀራመቱ ስግብግብ ዘረፊዎች መሬቱን ምን እንዳደረጉት ጥናት ያካሄዱ አሜሪካዊ ምሁር የሚከተለውን ሪፖርት አቅርበዋል…

More than 60% of crops grown on land bought by foreign investors in Ethiopia is intended for export, instead of for feeding local communities… the land is used to grow profitable crops – like sugarcane, palm oil, and soy. The benefits of this food  production “go to the investors and to the countries that are receiving the exports, and not to the benefit of local communities” Paolo D’Odorico, professor of environmental science at the university of Virginia.

(ውርስ ትርጉም) – ለባዕዳን ቱጃሮች ከተቸረው መሬት ከ60% በላይ የሚሆነው ምርት አገር ውስጥ ላለው ተመጋቢ ሳይሆን ለውጪ ገበያ ታስቦ እና ትርፋማነቱ ተሰልቶ የተመረተ ነው። መሬቱ ላይ የሚመረተው እንደ ስኳር ፣ የዘንባባ ዘይት እና ሶይ (በህንድ እና አረብ እንዲሁም በሩቅ ምስራቅ ተፈላጊነት ያለው) ምርት ነው። ከዚህ ምርት ቀጥተኛ ተጠቃሚው መሬት የዘረፉት ባለሀብቶች እና የምርቱ ተቀባይ የሆኑት አገራት ብቻ ናቸው። መሬቱን አሳልፈው የሰጡት ህሊና ቢስ ወያኔዎች ምን እንደሚጠቀሙ በዚህ ጥናት አልተጠቀሰም።

በዚህ ጭካኔ የተመላበት ወረራ ለም መሬቶች ለቅርምት ፣ ዜጎች ደግሞ ለእንግልት ፣ ለድህነት ተዳርገዋል። ዜጎች ከተፈጥሮ አከባቢያቸው በሀይል በጠመንጃ ተገደው ወደ ማያውቁት ፣ ለኑሮ ጨርሶ ተስማሚ ወዳልሆነ ስፍራ ተግዘዋል። የማፈናቀሉ ዘመቻ አፈፃፀም እጅግ ሰብአዊነት የጎደለው መሆኑን ለመግለፅ ያስቸግራል። እርምጃው ዛሬም አልተገታም… ወያኔ በስልጣን ላይ እስካለ ወረራው አይገታም።

አኑርዳህ ሚተል የሚባሉት የኦክላንድ ምርምር ተቋም ዋና አስተዳዳሪ ባለፈው  ዓመት ባቀረቡት ሪፖርታቸው ስለ ኢትዮጵያ የመሬት ቅርምት ሲገልፁ…

“investors (እነኝህ ባለሀብቶች) በኦሞ ሸለቆ የተንጣለለውን መሬት ወስደዋል። በደን የተከበበውን መሬት መርጠው ደኑን መንጥረው አካባቢውን ዱር አድርገውታል። ደን የተጨፈጨፈው ለልማት ነው ይላሉ ግን እኔን የማይገባኝ የተፈጥሮ ደን ምንጠራ እንዴት ከልማት ጋር እንደሚዛመድ ነው”

“The investors take land in the Omo Valley. They clear all land, choose the best place where trees are, leaving the area open. They say it is for development, but they are clearing the forests. I wonder how to reconcile development with forest destruction.”

ጣሊያናዊው የፎቶ ጋዜጠኛ አልፍሬዶ ቢኒ በበኩሉ ኢትዮጵያ ውስጥ ተዘዋውሮ ያገኘውን ሲያብራራ

 “These companies – mostly Saudi and Indian – are signing deals with the Ethiopian government to lease this land… for 25, 30 sometimes 50 years, depriving local population of the ability to harvest their crops and feed themselves. The government says the lands are empty and being harvested but from what I saw and documented in my reporting this is entirely not the case” Alfredo Bini an Italian photojournalist.

(ውርስ ትርጉም) “የኢትዮጵያ መንግስት ለም መሬቶችን ለሳውዲ እና ህንድ ኩባንያዎች ለ25 30 አንዳንዴም 50 አመት ለሚደርስ ኮንትራት (በባኮ ሲጋራ ዋጋ ነው ያለው መቶ አለቃ ተስፋ ገብራብ) ፈርሞ አስረክቧል። ይህን መሬት አርሰው ራሳቸውን ይቀልቡ የነበሩ ኢትዮጵያውያን ደግሞ ከአካባቢው ተባረዋል። መንግሰት ቦታው ጠፍ ነበር ማንም አይኖርበትም ነበር ይላል እኔ ባደረኩት ጥናት በደረስኩበት ጭብጥ ግን ይህ ፍፁም ውሸት ነው”።

የወያኔ ቀጣፊ ተፈጥሮ መላው አለም እንዲህ በይፋ እስከሚዘግበው ይፋ የሆነ ጉዳይ ነው። ዛሬ ጭራሽ ድንብርብራቸው ወጥቶ አንዱ ባለስልጣን የተናገረውን ሌላው እየተቃረነው ከዚህ ከዚያ ሲላተሙ እያየን ነው።

ሀያ ሚሊየን ህዝብ ላስቸኳይ የምግብ እርዳታ መጋለጡን በማያሻማ ቋንቋ ለመናገር እንኳ ድፍረት አላገኙም። ከለም መሬቶች ላይ የመፈናቀሉን ብሎም የተንሰራፋው ረሀብ ምን ድረስ እንደሆነ ለመዘገብ ወደ ስፍራው መጓዝ አይቻልም – ሙከራ ያደረጉትን የውጪ ጋዜጠኞችም መንገድ ላይ ጠብቆ በማሰር እና ማንገላታት የወያኔ ስራ ሆኗል። ይህ በአፄውም ሆነ በደርግ ዘመን ያልተደረገ አፈና ነው። የቢቢሲው ዲምብልቢን ሆነ ሌሎች የውጪ ጋዜጠኞች በደርግ ዘመን ድርቅ በመታቸው አካባቢዎች አላንዳች ተፅእኖ ተዘዋውረው የረሀቡን አስከፊነት ለመላው አለም እንዲያሳዩ ሙሉ ትብብር መደረጉ ይታወሳል።

በሚሊየን የሚቆጠሩ ዜጎች ዛሬ ለረሀብ የተጋለጡት ኤልኒኖ በተሰኘ የተፈጥሮ ሚዛን መዛባት ምክንያት ነው በሚል ወያኔ ሊራቀቅብን ይዳዳዋል። የተፍጥሮ አየር መዛባት የግድ ረሀብ አያመጣም – በአለም እጅግ ፈጣን ኢኮኖሚያዊ ዕድገት ታምር እያስመዘገብን ነን ከሚለው ጉራቸው ጋር ይህ እንዴት እንደሚታረቅ የሚያውቁት ወያኔዎች ብቻ ናቸው። ለማንኛውም ግን ህዝብ እንደ ቅጠል ከመርገፉ በፊት ተገቢው ሪፖርት በተለይ ነፃ በሆኑ የውጪ ጋዜጠኞች ሊጠናቀር ይገባዋል። አሜሪካንን ጨምሮ አንዳንድ ለጋሽ አገሮች ዳቦ ለተራበው ህዝብ ለማድረስ መዘጋጀታቸውን ገልፀዋል። እርዳታው ጊዜያዊ ማስታገሻ እንጂ ዘላቂ መፍትሔ እንዳልሆነ እነሱም ሁሉም ያውቃል – ህዝብ በጠመንጃ አፈሙዝ ስር የባርነት ቀንበር ተሸክሞ እያለ ሰው ሰራሽ በሆነ የአስተዳደር በደል እና የተዛባ ሀብት ስርጭት ሳቢያ የተተከለውን የድህነት ነቀርሳ መንቀል አይቻልም።

ያንድን እጅግ ድሀ ህብረተሰብ መሠረታዊ የዕድገት ደረጃ ፈር ለማስያዝ ወይም ወደ ላቀ እርከን ለማድረስ መሰረታዊ የሰብአዊ መብት ጥበቃ ቀዳሚ ቅድመ ሁኔታ ነው። በህዝብ ዘንድ ታማኒነት ያለው ፖቲካዊ ሥርዓት ለማናቸውም ዕድገት ቁልፍ መሆኑን የምሥራቁም ሆነ ምዕራቡ አለም ዕድገት ታሪክ የሚያረጋግጥ መሆኑን ላፍታ ልንዘነጋ አይገባም። እንደ ወያኔ አይነት ከህዝብ ጋር አይጥ እና ድመት ድብብቆሽ የሚጫወት መንግስት ግዙፍ ጠባሳውን ለመሸፈን አንዱን ሲያነሳ ሌላውን ሲጥል ዘመን ይቆጥራታል እንጂ የህዝቡን ህይወት አዎንታዊ በሆነ አቅጣጫ ለውጦ ዕድገት ሊያሰፍን ይችላል ማለት ዘበት ነው።

ወያኔ ጎጠኛ ነው – በዚህም ፀረ ብሔራዊ ፀረ ኢትዮጵያ ነው ፤ ወያኔ በዜጎች ሰብአዊ መብት አያያዝ ረገድ አፋኝ፣ አማቂ እና ገዳይ በመሆኑ ሕዝብ እንደ ወዳጅ ሳይሆን እንደ ማናቸውም ጉልበተኛ  ገዢ ብሎም ከብሔራዊ ጥቅም አንፃር እንደ ጠላት የሚያየው ሀይል ነው። እንደ ፖለቲካ ፓርቲ ከልደት እስከ ዛሬ ድረስ በህዝብ ዘንድ ከቶውንም አመኔታ ያጣ በሙስና የተበከለ ነው።

“Those basic human rights are not being upheld in Ethiopia. It is therefore urgent to make voices of those impacted heard.”  ኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች የተጨፈለቁባት አገር ናት። ስለሆነም የአፈናው ሰለባ የሆኑ ህዝቦች ድምፅ እንዲሰማ ማድረግ የሁላችንም አጣዳፊ ተግባር ሊሆን ይገባል ይሉናል ታዛቢዎች።

አንዳንድ ነጋዴዎች እስር ቤት አላቸው ነው ያለው ሀይለማርያም? አገር የሚያህል ክልል ህገ-ወጥ በሆነ አግባብ አስታቅፈህ ወህኒ ቢገነባበት ምን ይገርማል? እነ ካሪቱሪ 300ሺ ሄክታር መሬት ግዛታቸውን ለማስከበር ፀረ ልማት ሀይሎችን የሚቆጣጠሩበት እና የሚያስሩበት እስር ቤት የግድ ያስፈልጋቸዋል…

ሰሞኑን ከወያኔ ዜና መዋዕል አንብቤ ያስደመመኝን ጉዳይ ላካፍላችሁ እና ሀተታዬን ልደምድም — ጉዳዩ የወልቃይት ፀገዴን ማንነት የሚመለከት ነው። ወያኔ በየጊዜው ዳቦ ፍለጋ ወደ ወልቃይት እየፈለሱ የመጡ የትግራይ ተወላጆችን ሰልፍ እንዲወጡ ያደርጋል –

እነኝህ ወልቃይት ፀገዴ ላይ ሰልፍ የወጡ ነዋሪዎች ካነገቡት መፈክር መካከል “በህወሃት መስዋትነት የተረጋገጠው ማንነታችን በጥቂት ፀረ ሰላም ሃይሎች አይደናቀፍም” ይላል። እንደ ሰልፈኞቹ እና አሰላፊዎቹ ከሆነ የወልቃይት ማንነት ህወሃት አስራሰባት አመታት ከመታገሉ በፊት አይታወቅም ነበር ማለት ነው። ወያኔ አስራሰባት አመት ታግሎ መስዋዕትነት ባይከፍል ኖሮ የወልቃይት ማንነት መና ቀርቶ በቀረ ነበር። እንደ ሰልፈኞቹ መፈክር ከሆነ ግን ማንነቱ አይታወቅ እንጂ ወልቃይት የሚባል ቦታ እና ሰዎች ድሮም ነበሩ – የሆኑ ሰዎች ፣ ማንነታቸው ያልተረጋገጠ ሰዎች ወልቃይት ውስጥ ነበሩ እንደማለት። ወያኔ ግን አስራ ሰባት አመታት ታግሎ ማንነት አጎናፀፋቸው…

“በህወሃት መስዋትነት የተረጋገጠው ማንነታችን በጥቂት ፀረ ሰላም ሃይሎች አይደናቀፍም” ይላሉ ዳቦ ፍለጋ መጥተው መሬት ቀማኛ የሆኑት ሰፋሪዎች።

በዚህ አያያዝ ጋምቤላ ላይ ካሪቱሪ የተረከበው የ300ሺ ሄክታር ክልል ማንነት ህንድ ነው ቢባል አሜን ብለን መቀበል ይጠበቅብናል ማለት ነው። ምክንያቱም በአስራሰባት አመታት የወያኔ መስዋዕትነት ባይሆን ኖሮ ካሪቱሪን ማን ጋምቤላ ያደርሰው ነበር? ካሪቱሪ አሁን የ300ሺ ሄክታር መሬት ባለቤት መሆኑ ተረጋግጧል – ካሪቱሪ ደግሞ ህንድ ነው። 300ሺ ሄክታር መሬት ያገኘሁት ህወሃት 17 ዓመታት ታግሎ በከፈለው መስዋዕትነት ነው ቢል ማን ይጠይቀዋል – ካገሩ ያመጣቸውን ህንዶች አሰልፎ ‘…ማንነታችን በጥቂት ፀረ ሰላም ሃይሎች አይደናቀፍም’ ቢልስ ምን ችግር አለው። ጋምቤላ ህንድ ፣ ወልቃይትም ትግራይ የሆኑት በአስራሰባት አመት የወያኔ መስዋዕትነት ነው ብለን ዝም እንድንል ይጠበቅብናል። ጋምቤላ የትግራይ ኩታ ገጠም አለመሆኑ በጅቶታል።

የማንነት ጥያቄ ላንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ተፈቷል ነው ያሉት ክቡር ጠ/ሚኒሰትሩ?

ወይ ነዶ!!

The post ዳቦ ለተራቡ ፣ መሬት ለጠገቡ! | ታሪኩ አባዳማ appeared first on Zehabesha Amharic.

የትግራይ አስተዳደር በ30 ሚልዮን ብር የሙስና ክስ ሊቀረበበት ነው

$
0
0

አምዶም ገብረሥላሴ እንደዘገበው

የውሃና ኢነርጂ ምኒስቴር ለትግራይ ክልል መስተዳድር የ30 ሚልዮን ብር ሙስና ክስ ሊያቀርብበት ዝግጅቱ ማጠናቀቁ ታውቋል።
የ30 ሚልዮን ብር ክሱ በራያ ለመስኖ ስራ እንዲውል ተብሎ በፌደራል የውሃና ኢነርጂ ምኒስቴር በጀት ተይዞ የነበረ ሲሆን ምንም ሳይሰራበት የተዘረፈ ብር ነው።

tsegaye-berehe (1)
ምኒስቴሩ በጀቱ የውሃ ጉድጓድ ተቆፍረው ገበሬዎች ለተለያየ የመስኖ ስራዎች የሚያገለገሉባቸው ፕላስቲክ ቱቦላሪዎች ከውጭ እንዲገዛ የታቀደ ሲሆን በወቅቱ የትግራይ ክልል የውሃና መኣድን ቢሮ ሃላፊ የነበረው ኣቶ ጌታቸው የተባለ የኣቶ ፀጋይ በርሀ የእህታቸው ልጅ ጥራት የጎደለው እቃ ካስገባና ከጥቅም ውጭ መሆናቸው ከተረጋገጠ በኋላ ብሩ ይዞ ጃፓን ኣገር መግባቱ የሚታወቅ ነው።
ብሩ በመዘረፉ ምክንያት የመስኖ ስራው ሙሉ በሙሉ ከጥቅም ውጭ የሆነ ሲሆን ብሩ ዘርፎ ጃፓን የገባው የኣቶ ፀጋይ በርሀ የእህት ልጅ የሆነው ኣቶ ጌታቸው በቁጥጥር ስር ለማስገባትም ምንም ዓይነት ሙከራ ኣልተደረገም።
ምኒስቴሩ ኣሁን በትግራይ ክልል መስተዳድር እየመሰረተው ያለው ክስ 30 ሚልዮን ብሩ ሙስና ዙርያ የወቅቱ የትግራይ ክልል ኣስተዳዳሪዎች እጅ ኣላቸው የሚል ነው።
የትግራይ ክልል በፌደራልና በክልል መንግስት የሚበጀት በሚልዮን የሚገመት ብር በሃላፊዎች እየተዘረፉ ፕሮጀክቶች ተጀምረው ሳይጠናቀቁ በቁም የሚቀሩባት ክልል ናት።
በኣሁኑ ወቅት ህወሓትና ሙስና፣ ሙስናና ህወሓት ተነጣጥለው የማይታዩ የኣንድ ሳንቲም ሁለት ገፆች መሆናቸው ተረጋግጠዋል።
ነፃነታችን በእጃችን ነው።
it is so.

The post የትግራይ አስተዳደር በ30 ሚልዮን ብር የሙስና ክስ ሊቀረበበት ነው appeared first on Zehabesha Amharic.

ቤልጂየም ብራሰልስ በሁለት ፍንዳታዎች ተናጠች |ከ18 ሰዎች በላይ ሞተዋል |ቪድዮም ይዘናል

$
0
0


(ዘ-ሐበሻ) የአውሮፓ ሕብረት መቀመጫ የሆነችው ቤልጂየም ብራሰልስ የአሸባሪዎች ጥቃት ደረሰባት:: በሁለት ቦታዎች በተከታተይ በደረሰ ፍንዳታ እስካሁን 18 የሚያህሉ ሰዎች መሞታቸው የሃገሪቱ የመገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል::

የመጀመሪያው ፍንዳታ ዛሬ ማክሰኞ ጠዋት የደረሰው በቤልጂየም ብራሰልስ አውሮፕላን ማረፊያ የመንገደኞች መመለሻ ህንፃ ውስጥ ሲሆን የ18 ሰዎችን ሕይወት ሲቀጥፍ ከ30 ሰዎችን በላይ አቅሱሏል:: ሁለተኛው ፍንዳታም የሃገሪቱ የባቡር መንገድ መጠበቂያ ላይ መደረሱን ዘ-ሐበሻ ከሃገሪቱ ሚድያዎች ያገኘችው መረጃ ያሳያል:: የሟቾች ቁጥር ከዚህም በላይ ክፍ ሊል ይችላል::

Still image shows black smoke rising from the Brussels airport following explosions

ይህ ፍንዳታ ከመድረሱ አስቀድሞ በአረብኛ ጫጫታዎች ይሰሙ እንደነበርና የተኩስ ልውውጥ እንደበር የሚያስረዱት የዜና ምንጮቹ በፓሪስ ባለፈው ኖቨምበር በአሸባሪዎች አደጋ ለ130 ሰዎች መጥፋት ከሆኑት ተጠርጣሪ አሸባሪዎች መካከል አንዱ ከ4 ቀን በፊት ከመያዙ በኋላ እነዚህ ሁለት ፍንዳታዎች መከሰታቸው ጉዳዩን ከዚሁ ጋር እንዳያያዘው የኖርዌይ ሚድያዎች ዘግበዋል::

ለፓሪሱ ጥቃት ተጠርጣሪ የሆነው ግለሰብ በኖርዌይ ከተይዘ በኋላ የሃገሪቱ ፖሊስ በተጠንቀቅ ላይ እንደነበር የሚገልጹት ምንጮቹ ሆኖም ግን ሁለቱን ፍንዳታዎች ከመከሰታቸው በፊት አላስቆሟቸውም ብለዋል::

The post ቤልጂየም ብራሰልስ በሁለት ፍንዳታዎች ተናጠች | ከ18 ሰዎች በላይ ሞተዋል | ቪድዮም ይዘናል appeared first on Zehabesha Amharic.

በሕወሓት መንግስት በዳንሻ ላይ እየተፈጸመው ስላለው ግፍ ከዉስጥ አርበኞች የተሰጠ ማስጠንቀቂያ

$
0
0

የትግራይ ነጻ አዉጪ ቡድን መጠቀሚያና መሳሪያ በመሆን እያገለገሉ የሚገኙት አንዳንድ የእምነት ተቋማትንና መሪዎችን እንዲሁም ሽማግሌዎችን መሰረት ባደረገ መልኩ በዳንሻ ህዝብ ላይ እርቅ በሚል ሰበብ ግፍ እየተሰራ መሆኑን ደርሰንበታል!
clash
ግፍም እየተፈጸመባቸዉ የሚገኙ አማራ ኢትዮጵያዊያንን ጎብኝተናል!

ይህ እንዲሆን ምክንያታዊ መጠቀሚያ የሆናችሁ ግለሰቦች እራሳችሁን እንድትፈትሹ እያስጠነቀቅን!!

ከእንግዲህ የወልቃይት ጠገዴን አማራ የማንነት ጉዳይ እና ተዛማጅ የመብት ጥያቄዎችን ያነሱ ወገኖቻችንን በእርቅም ሆነ በማንኛዉም ሰበብ በማታለል ለጎጠኛዉ የትግራይ ሽፍታ አሳልፋችሁ የምትሰጡ የሐይማኖት ተቋማት አባቶች የሐገር ሽማግሌ ተብዬዎች ከእኩይ ተግባራችሁ እንድትታቀቡ እያሳሰብን።

በታገቱና በተገደሉብን ወገኖቻችን እጥፍ ምላሽ ከመስጠት አንጻር እንዲሁም ሆን ብለዉ የዳንሻ ህዝብ ላይ አፈናዉ እና ግድያዉ እንዲጠናከር ባደረጉ እና በተዛማጅ ከወያኔ ጋር ንክኪ ባላቸው ግለሰቦች ላይ እርምጃ መዉሰድ ጀምረናል ይህም ተጠናክሮ ይቀጥላል !!

ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ ! !

The post በሕወሓት መንግስት በዳንሻ ላይ እየተፈጸመው ስላለው ግፍ ከዉስጥ አርበኞች የተሰጠ ማስጠንቀቂያ appeared first on Zehabesha Amharic.


የጋዜጠኛና ደራሲ ሙሉጌታ ሉሌ መታሰቢያ ዝግጅት |ሚያዝያ ፩ ቀን ፳፻፰ ዓ/ም (April 9, 2016)

$
0
0

mulugeta lule
የጋዜጠኛና ደራሲ ሙሉጌታ ሉሌ መታሰቢያ ዝግጅት

ሚያዝያ ፩ ቀን ፳፻፰ ዓ/ም (April 9, 2016)

አንጋፋው ጋዜጠኛ፣ ሃያሲ፣ ደራሲና የፖለቲካ ተንታኝ ሙሉጌታ ሉሌ በብዕሩ ሀገራዊ ፍቅርን፣ አንድነትን ነፃነትን፣ ያንጸባረቀ፤ በአንደበቱ ስለ ኢትዮጵያ የመሰከረ፤ እስከ መጨረሻ እስትንፋሱ ድረስ ኢትዮጵያን ያገለገለ፤ ኢትዮጵያን ተቀምቶም በስደት የቀረ ሀገራዊ ሀብት ነበረ::

ታላቁ ብዕረኛ ሙሉጌታ ሉሌ በኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት፣ በመነን፣ በጦቢያ እና በልሳነ ሕዝብ መፅሔቶች አገልግሏል:: እንዲሁም በኢትዩጵያ ቴሌቪዥን ኔትወርክ (ኢቴን) እና በኢትዮጵያ ሳተላይት ቴሌቪዥንና ሬዲዮ (ኢሳት) አገልግሏል። በዚህም ስለ ሰው ልጅ መብት፣ ፍትሃዊነት፣ ነፃነት፣ እኩልነትና ዲሞክራሲያዊ ሥርዓት መስፈን ብሎም መከበር ያለመታከት ሲያስተምር ኖሯል። ስለ ነጻነት የሚሰብከው ያ አንደበት ዛሬ ባይኖርም፣ እውነትና እውቀትን የሚ዗ራው ብዕር ዛሬ ቢቋረጥም፣ ሥራው ግን ህያው ሆኖ ከመቃብር በላይ ሲታወስ ይኖራል።

ጋዜጠኛና ደራሲ ሙሉጌታ ሉሌ በሕይወት ዘመኑ ለሀገርና ለሕዝብ ላበረከተው አስተዋጽዖ ለማመስገን እና ሕያው ሥራዎቹንም ለዘመ዗ከር ታላቅ ሕዝባዊ የመታሰቢያ ፕሮግራም ተ዗ጋጅቷል። እርስዎም በዚያ ታላቅ ዝግጅት ላይ እንዲገኙልን በአክብሮት ጋዘብ዗ንዎታል።

የጋዜጠኛና ደራሲ ሙሉጌታ ሉሌ መታሰቢያ ልዩ ልዩ ዝግጅቶችየ ሚቀርቡበት ቀን:- ሚያዝያ 1 ቀን 2008 ዓ/ም (April 9, 2016)
ሰዓት 2:30PM – 6:00 PM
ቦታ:- Marriot Hotel (Crystal Gateway) 1700 Jeferson Davis Hwy Arlington, VA
ከሙሉጌታ ሉሌ የመታሰቢያ ዝግጅት ኮሚቴ


The post የጋዜጠኛና ደራሲ ሙሉጌታ ሉሌ መታሰቢያ ዝግጅት | ሚያዝያ ፩ ቀን ፳፻፰ ዓ/ም (April 9, 2016) appeared first on Zehabesha Amharic.

ኢህአዴግ ላልተወሰነ ጊዜ መሬት እደላ ማቆሙና አላሙዲን |የዋዜማ ራድዮ ዜና ትንታኔ

$
0
0

የኢትዮዽያ መንግስት ብዙ ተስፋ የጣለበትንና የውጪ ምንዛሪ እንደሚያመጣ የተነገረለት የሰፋፊ እርሻ ኢንቨስትመንት ውድቀት ገጥሞታል። መንግስት ላልተወስነ ጊዜ መሬት መስጠት ማቆሙን አስታወቋል። በኦሮሚያ የተቀሰቀሰው ከመሬት ጋር የተያያዘ ቀውስና የድርቅ አደጋ ኢህአዴግ በመሬት ጉዳይ አቋሙን እንዲመረምር ግድ ሳይለው አልቀረም። ቻላቸው ታደሰ ያዘጋጀውን ዘገባ እነሆ።

በተለይ በሼክ ሙሃመድ አላሙዲን ባለቤትነት በተያዘው ሳዑዲ ስታር እርሻ ላይ ያተኮረው የፋይናንሻል ታይምስ ጥናት እንደሚያሳየው ባለሃብቱ በጋምቤላ ክልል ከ20 ሺህ እግር ኳስ ሜዳዎች ጋር የሚስተካከል ለም መሬት ይዘዋል፡፡ ይህም ቱጃሩን ከዓለም ግንባር ቀደም ለም መሬት ተቀራማቾች ተርታ እንደሚያሰልፋቸው ያትታል፡፡

በተለይ በሼክ ሙሃመድ አላሙዲን ባለቤትነት በተያዘው ሳዑዲ ስታር እርሻ ላይ ያተኮረው የፋይናንሻል ታይምስ ጥናት እንደሚያሳየው ባለሃብቱ በጋምቤላ ክልል ከ20 ሺህ እግር ኳስ ሜዳዎች ጋር የሚስተካከል ለም መሬት ይዘዋል፡፡ ይህም ቱጃሩን ከዓለም ግንባር ቀደም ለም መሬት ተቀራማቾች ተርታ እንደሚያሰልፋቸው ያትታል፡፡

የኢትዮጵያ መንግስት ለኢንቨስተሮች ለግብርና ስራ የሚውሉ ሰፋፊ ለም መሬቶችን ላልተወሰነ ጊዜ መስጠት ማቆሙን ገልጧል፡፡ ላለፉት በርካታ ዓመታት ፌደራል መንግስቱ በውክልና የክልሎችን ሰፋፊ ለም መሬቶች ተረክቦ ለውጭ ባለሃብቶችና ዓለም ዓቀፍ የእርሻ ኮርፖሬሽኖች በርካሽ በሊዝ ሲያከራይ መቆየቱ ብርቱ ትችት አስከትሎበት ነበር፡፡ ሆኖም መንግስት ትችቶቹ ሁሉ “የሀገሪቱን ዕድገት ማየት የማይፈልጉ ኃይሎች ሴራ” ናቸው በማለት ሲያጣጥል ቢቆይም በድንገት ግን ፖሊሲውን ለመፈተሸ ተገዷል፡፡  መንግስት ፖሊሲውን እርግፍ አድርጎ ባይተወውም በዘርፉ የታዩ ችግሮችን ገምግሜ መፍትሄ እስከምሰጥ ድረስ ላልተወሰነ ጊዜ ለም መሬት ለባለሃብቶች መስጠቴን አቁሚያለሁ ብሏል፡፡

ጠቅላይ ሚንስትሩ ቀደም ሲል ሰፋፊ እርሻዎች ለባለሃብቶች ወደ ተሰጡባቸው ክልሎች የጥናት ቡድን መላካቸውን የዘገበው ራዲዮ ፋና የአሁኑ ውሳኔ የዚያ ጥናት ውጤት መሆን አለመሆኑን አልገለፀም፡፡

መንገድ የለም… ሰባራ ሳንቲም የለም….

መንግስት እዚህ ውሳኔ ላይ እንዴት ሊደርስ ቻለ? የሚለውን ጥያቄ መፈተሸ ያስፈልጋል፡፡ እንደ ፋና ዘገባ ከሆነ ለፖሊሲ ለውጡ እንደምክንያት የቀረበው የግብርና ኢንቨስትመንት እና መሬት አስተዳደር ኤጀንሲ በአራት ክልሎች በአደራ ከተረከበው ለም መሬት 470 ሺህ ሄክታሩን ለ131 ባለሀብቶች ቢሰጥም ውጤታማ የሆኑት ግን ከ30 በመቶ ብቻ መሆናቸው ነው፡፡ ጉዳዩ በቀጥታ ከሚመለከታቸው መንግስት መስሪያ ቤቶች የተገኙ መረጃዎች እንደሚያሳዩት ግዙፍ እርሻ አልሚዎቹ ውጤታማ ሊሆኑ ያልቻሉት ዘመናዊ የእርሻ መሳሪያዎችንና የሰው ሃይልን ለም መሬቶች ወደሚገኙባቸው ሩቅ ቦታዎች ለማድረስ ባለመቻላቸውና ሰባት ያህል የውጭ ኢንቨስተሮችም በቅርቡ ፍቃዳቸው በመሰረዙ እንደሆነ መረጃዎች ያሳያሉ፡፡ መንግስት ከዘርፉ አገኛለሁ ብሎ የጠብቀው የውጭ ምንዛሬም እንደታሰበው አለመሆኑ የመንግስትን ፖሊሲ አጣብቂኝ ውስጥ ያስገባ ሌላኛው ምክንያት እንደሆነ ታዛቢዎች ያስረዳሉ፡፡

ህንዶቹ… መጡ? ሄዱ?

ምንም እንኳ የአሁኑ የመንግስት ውሳኔ ድንገተኛ ቢመስልም በመንግስትና በግዙፎቹ እርሻ ኢንቨስተሮች መካከል ያለው ግንኙነት እየሻከረ መመምጣቱ የታወቀው ግን ቀደም ብሎ ነበር፡፡ በተለይ በጋምቤላ ክልል 25 ሺህ ሄክታር ተረክቦ የነበረው የህንዱ ሳበር፣ 5 ሺህ ሄክታር የነበረው ሌላኛው የህንድ ኩባንያ ጄ.ቪ.ኤል እና ግዙፉ ካራቱሪ ግሎባል ኩባንያ ፍቃዳቸው ከተሰረዘባቸው በኋላ፡፡

ባለፈው ታህሳስ ወር ደግሞ ግንኙነቱ ማሽቆልቆሉና የመንግስት መከራከሪያ ውሃ የማይቋጥር መሆኑ የተጋለጠው በጋምቤላ ክልል 100 ሺህ ሄክታር ተረክቦ የነበረው በዓለም በፅጌረዳ አበባ አምራችነቱ የሚታወቀው የህንዱ ካራቱሪ ከሁለት ዓመት በኋላም ስራ መጀመር ባለመቻሉ መንግስት መሬቱን ነጥቆ ወደ መሬት ባንክ ገቢ ሲያደርግ ነው፡፡ ካራቱሪ ገና ከማለዳው 300 ሺህ ሄክታር ተረክቦ በኋላ ግን ወደ 100 ሺህ ሄክታር ዝቅ መደረጉ መንግስት የኩባንያዎችን አቅም ግምት ውስጥ ሳያስገባ በደመ-ነፍስ ለም መሬት ሲሸነሽን እንደኖረ ማሳያ ሊሆን ይችላል፡፡ ካራቱሪ ግን በመንግስት ያላግባብ የተጣሰውን መብቴን በዓለም ዓቀፍ ህግ አስከብራለሁ እያለ መዛቱን አላቆመም፡፡

መንግስት ግልፅነት የጎደለውን ግዙፉን የለም መሬት ኪራይ በረከት ይዞ መጥቷል እያለ ለማሳመን ቢለፋም ፖሊሲው በአብዛኛው ህዝብ ዘንድ በጥርጣሬ ይታያል፡፡ ሰፋፊ እርሻዎቹ ለሀገሪቱ ምግብ ዋስትና መሻሻል ጠብ የሚደርጉት አስተዋፅዖ አለመኖሩ ደግሞ ጥርጣሬውን አባብሶት ቆይቷል፡፡

በያዝነው ዓመት በሀገሪቱ መጠነ-ሰፊ ድርቅ ሲከሰት በወጭ ንግድ ላይ ለተሰማሩ አትራፊ ግዙፍ ኩባንያዎች ለም መሬት ሲሸነሽን የኖረው መንግስት ወደያውኑ ዓለም ዓቀፍ ለጋሾች ምግብ ዕርዳታ እንዲለግሱት መማፀኑ የመንግስት ምግብ ዋስትና ፖሊሲ ውድቀት ማሳያ እንደሆነ ታዛቢዎች ይናገራሉ፡፡

ከውጭ ባለሃብቶች የግብርና ቴክኖሎጂ ሽግግር ማግኘት ይቻላል በማለት ሲከራከር የኖረው መንግስት አሁን ግን አመርቂ ውጤት ስላልተገኘበት አሰራሩን ላቆመው ወስኛሁ ማለቱ ብዙዎችን ማስገረሙ አይቀርም፡፡ በዘርፉ የሚታዩ ችግሮችን ሲያድበሰብስ ቢኖርም በአስተዳደራዊ ችግሮች ሳቢያ ምክንያት ታች አምና ብቻ 43 መሬቶች ለተለያዩ ባለሃብቶቸ ተሰጥተው፣ መሬቶቹን የተረከቡ ባለሃብቶችም ለተመሳሳይ መሬት ከባንክ ተደራራቢ ብድር ወስደው መገኘታቸውን አምኗል፡፡ አበዳሪዎቹ የመንግስት ባንኮች ግን ለሰፋፊ እርሻ ልማት የሚሰጡት ብድሩ ምን ላይ እንደዋለ ማወቅ ያልቻሉበት ሁኔታ መፈጠሩን አምኗል፡፡  ባንኩ ባለፉት አምስት ዓመታት ውስጥ ብቻ ለሰፋፊ እርሻ ልማት ስድስት ቢሊዮን ብር አበድሯል፡፡ በመንግስት ፖሊሲ ድክመት ሳቢያ ባንኮች የገጠማቸው መጠነ-ሰፊ ኪሳራ ወደፊት ይታወቅ እንደሆን እንጂ እስካሁን የተሟላ መረጃ የለም፡፡ መንግስትን በፓርላማ ተጠያቂ የሚያደርግ አሰራር ባለመዘርጋቱ እንጂ ግዙፍ የመሬት ኢንቨስትመንት ፖሊሲው ከፍተኛ ውድቀት እንደሚያስከትል የዘርፉ ባለሙያዎች ማስጠንቀቅ የጀመሩት ገና ከማለዳው ነበር፡፡

በታዳጊ ሀገሮች የሚደረገውን መሬት ቅርምት ያባባሰው በሰለጠነው ዓለም ከገጠር ወደ ከተማ የሚፈልሱ ሰዎች ቁጥር እየጨመረ ሲሄድ በምርት አቅርቦትና ምግብ ፍላጎት መካከል ያለው ክፍተት እየሰፋ በመምጣቱ እንደሆነ መረጃዎች ያመለክታሉ፡፡ በተለይ እኤአ የ2007ቱ ዓለም ዓቀፍ የምግብ ሰብል ዋጋ ንረት እና የ2008ቱ ዓለም ዓቀፉ የፋይናንስ ቀውስ መንግስታትና ዓለም ኣቀፍ ኮርፖሬሽኖችን በተለምዶ ከሚታወቁት የኢንቨስትመንት ዘርፎች ወጣ ብለው በታዳጊ ሀገሮች ለም መሬቶች ላይ በቢሊዮን የሚቆጠር ኢንቨስትመንት እንዲጀምሩ ገፋፍቷቸዋል፡፡

በተለያዩ ዓለም አቀፍ ድርጅቶች ጥናት ሲነገር እንደኖረው በዓለም አቀፉ መሬት ሽሚያ ኢትዮጵያን የተለየ የሚያደርጋት ለም መሬቷን በገፍ ማቅረቧ ብቻ ሳይሆን መንግስት የሚያቀርበው ዓመታዊ የመሬት ኪራይ ዝቅተኛ በመሆኑ ጭምር ነው፡፡ ሳዑዲ ስታር እንኳ በሄክታር የሚከፍለው ዓመታዊ ኪራይ ስልሳ ብር ወይም ሶስት ዶላር ብቻ ነው፡፡ ኢንቨስተሮቹ የታክስ እፎይታ ጊዜ እና የባንክ ብድርም ተጠቃሚ ሲሆኑ ቆይተዋል፡፡ ለሰፋፊ እርሻ ኢንቨስትመንት ጀርባውን ሰጥቶ የኖረው ኢህአዴግ-መራሹ መንግስት የዛሬ አስር ዓመት አካባቢ መሰረታዊ የፖሊሲ ለውጥ በማድረጉ ኢትዮጵያ በአወዛጋቢውና ውስብስቡ  የመሬት ቅርምት ስሟ በቀዳሚነት እንዲነሳ አድርጓታል፡፡

ባለፉት ጥቂት ዓመታት ብቻ ከቻይና፣ ህንድ፣ ሱዳን፣ ሳዑዲ ዓረቢያ፣ ቱርክና ፓኪስታን የመጡ ከሃምሳ በላይ ኢንቨስተሮች  በተለያዩ ክልሎች መሬቶችን ይዘዋል፡፡ በተለይ ምግባቸውን ከውጭ የሚያስገቡት ቱጃሮቹ የዓረብ ሀገራት ኢትዮጵያ፣ ሞዛምቢክ፣ ዛምቢያ፣ ሱዳንና ታንዛኒያን በመሳሰሉ የአፍሪካ ሀገሮች ለም መሬት በመቀራት ላይ ተጠምደው ኖረዋል፡፡ የኢትዮጵያ መንግስትም የአሁኑን ድንገተኛ ለውጥ እስካደረገበት ዕለት ድረስ በጠቅላላው 3.3 ሚሊዮን ሄክታር ለም መሬት በሊዝ ለማቅረብ ዝግጅቱን ማጠናቀቁን ሲሰብክ ነበር፡፡

መንግስት ለም መሬቶችን ለኢንቨስተሮች ለማስለቀቅ ሲል በጋምቤላና ደቡብ ኦሞ በሺዎች የሚቆጠሩ ነዋሪዎችን “አስገድዶ በሌሎች ቦታዎች አስፍሯል፤ በሂደቱም ሰብዓዊ መብቶችን ጥሷል” በማለት ኦክላንድ ኢንስቲትዩትና ሂውማን ራይትስ ዎች የሰላ ውንጀላ ያቀርቡበታል፡፡ ኣለም ባንክም የመንግስትን ፕሮጄክት አግዟል የሚል ውንጀላ ቀርቦበት በያዝነው ዓመት ፖሊሲውን እንደገና ለመፈተሽ መገደዱ ይታወሳል፡፡ መንግስት ግን የሰፈራዎቹ ዓላማ መሰረታዊ ማህበራዊ አግልግሎቶችን ለዜጎች ለማዳረስ እንጂ ከመሬት ቅርምት ጋር ምንም ግንኙነት የላቸውም በማለት ሽንጡን ገትሮ ከመከራከር አልቦዘነም፡፡

ፓርቲውና አል አሙዲን

በያዝነው ወር መጀመሪያ ላይ ፋይናንሻል ታይምስ የተሰኘው ታዋቂው የእንግሊዝ ጋዜጣ በመልቲ ሜዲ ክፍሉ አማካኝነት ዓለም ዓቀፍ የእርሻ ኢንቨስተሮች በኢትዮጵያ በሚያደርጉት ግዙፍ የመሬት ቅርምት ላይ ባጠናበት ሪፖርቱ ገዥው ፓርቲ ሰፋፊ ለም መሬቶችን በገፍ ለውጭ ኢንቨስተሮች የሚያከራየው በመሬት ላይ ያለውን ባለቤትነት አስጠበቆ ለመቀጠል እንዲያመቸው ሊሆን እንደሚችል ያለውን ጥርጣሬ አልሸሸገም፡፡ በኢትዮጵያ የመሬት ባለቤትነት የፖለቲካ ስልጣን ማስጠበቂያ መሆኑ ይታወቃል፡፡

በያዝነው ወር መጀመሪያ ላይ ፋይናንሻል ታይምስ የተሰኘው ታዋቂው የእንግሊዝ ጋዜጣ በመልቲ ሜዲ ክፍሉ አማካኝነት ዓለም ዓቀፍ የእርሻ ኢንቨስተሮች በኢትዮጵያ በሚያደርጉት ግዙፍ የመሬት ቅርምት ላይ ባጠናበት ሪፖርቱ ገዥው ፓርቲ ሰፋፊ ለም መሬቶችን በገፍ ለውጭ ኢንቨስተሮች የሚያከራየው በመሬት ላይ ያለውን ባለቤትነት አስጠበቆ ለመቀጠል እንዲያመቸው ሊሆን እንደሚችል ያለውን ጥርጣሬ አልሸሸገም፡፡ በኢትዮጵያ የመሬት ባለቤትነት የፖለቲካ ስልጣን ማስጠበቂያ መሆኑ ይታወቃል፡፡

በተለይ በሼክ ሙሃመድ አላሙዲን ባለቤትነት በተያዘው ሳዑዲ ስታር እርሻ ላይ ያተኮረው የፋይናንሻል ታይምስ ጥናት እንደሚያሳየው ባለሃብቱ በጋምቤላ ክልል ከ20 ሺህ እግር ኳስ ሜዳዎች ጋር የሚስተካከል ለም መሬት ይዘዋል፡፡ ይህም ቱጃሩን ከዓለም ግንባር ቀደም ለም መሬት ተቀራማቾች ተርታ እንደሚያሰልፋቸው ያትታል፡፡

ለአሁኑ የመንግስት ውሳኔ ኢኮኖሚያዊ ምክንያቶች እንደተጠበቁ ሁነው መንግስት ከመሬት ጋር በተያያዘ የተነሳው በኦሮሚያ ክልል የተነሳው ህዝባዊ አመፅ ወደሌሎች ክልሎችም እንዳይጋባ ስጋት አድሮበት ሊሆን ይችላል፡፡ እንደ ሂውማን ራይተስ ዎችና ኦክላንድ ኢንስትቲዩት ያሉ የመብት ተሟጋች ዓለም ኣቀፍ ድርጅቶችም በመንግስት ላይ የሚያቀርቡት ውንጀላ ተባብሶ መቀጠሉም አስተዋፅዖ አይኖረውም ለማለት ያስቸግራል፡፡

ምንም እንኳ በመንግስት ብዙ ባይነገርለትም በተለይ በጋምቤላ አኝዋኮች በሚያዝያ 2004 በሩዝ አምራቹ ሳኡዲ ስታር እርሻ ላይ ጥቃት ፈፅመው አምስት ሰራተኞችንመግደላቸው ለመንግስትም ሆነ ለቱጃሩ ማስጠንቀቂያ ደወል ነበር፡፡ ከሀገሪቱ ክልሎች ከፍተኛ መጠን ያለው ለም መሬት ለውጭ ኢንቨስተሮች የተሰጠባት ጋምቤላ ግዙፎቹ የዓለም ዓቀፉ ገበያ ሃይሎች ከዘልማዳዊው አኗኗር ዘይቤ ጋር በቀጥታ የተላተሙባት ዓይነተኛ ማሳያ ሆናለች፡፡ የመሬት ቅርምቱ ወደፊት ግጭት ቀስቃሽ እንደሚሆን ዓለም ኣቀፍ ተቋማት የሚያስጠነቅቁትም  ይህንን ግጭት መነሻ በማድረግ ነው፡፡ ፋይናንሻል ታይምስም በሪፖርቱ ምንም እንኳ ባለሃብቶች በተለያዩ ሀገሮች ቴክኖሎጂና ስራ ዕድሎችን ለማቅረብ ተስፋ ቢሰጡም መሬት ግን በቀላሉ ሊያለምዱት ከማይችሉት አንበሳ ጋር ተመሳስሎባቸዋል በማለት መሬት ለገጠር ገበሬዎች ሸቀጥ ሳይሆን የምግብ ዋስትና ምንጭና የማህበራዊ ማንነታቸው መሰረት መሆኑን ያሰምረበትም ለዚህ ነው፡፡

በ2009 ለሃምሳ ዓመታት 10 ሺህ ሄክታር ለም መሬት በሊዝ በመግዛት በጋምቤላ ክልል ስራውን የጀመረው ሳዑዲ ስታር ለተወሰኑ ዓመታት አጣብቂኝ ውስጥ ገብቶ ቢንገዳገድም ብዙም ሳይቆይ ግን አራት ሺህ ሄክታር ለም መሬት በመጨመር የሩዝ ሰብል ምርቱንና ትርፍ ማካበቱን አጧጡፎታል፡፡ በጠቅላላው ከ2 ነጥብ አምስት ሚሊዮን ሄክታር በላይ ለም መሬት የወሰደው ሳዑዲ ስታር ከፓኪስታንና ህንድ ያስመጣቸውን ምርጥ የሩዝ ዘሮች በማዳቀል 62 ያህል ምርጥ ዘሮችን አዘጋጅቶ የተወሰኑት ዝርያዎች ለሀገር ውስጥ ገበያ ያሰበ ሲሆን ቀሪዎቹን ምርጥ ዝርያዎቹ ግን ለውጭ ገበያ ለመላክ እንዳሰበ መረጃዎች ይገልፃል፡፡ ሩዝ ምርቱን እስካሁን ከሀገር ውስጥ ገበያ አልፎ አንድም ፍሬ ሩዝ ለውጭ ገበያ እንዳላቀረበ የሚከራከረው ሳዑዲ ስታር በመጭዎቹ ሁለት ዓመታትም 100 ሚሊዮን ዶላር ኢንቨስት በማድረግና 21 ኪሎ ሜትር ርዝማኔ ያለው የመስኖ ቦይ በመገንባት ዓመታዊ የሩዝ ምርቱን 140 ሺህ ቶን ለማድረስ ማቀዱን የፋይናንሻል ታይምስ ሪፖርቱ ይጠቅሳል፡፡ ይህም የኢትዮጵያን ዓመታዊ የሩዝ ፍላጎት ማሟላት የሚችል የምርት መጠን ያህል እንደሆነ ይገመታል፡፡ ሳዑዲ ስታር መስኖ ውሃ የሚጠልፈው በሩሲያ ዕርዳታ በደርግ ጊዜ በአልዌሮ ወንዝ ላይ ከተገነባው ትልቁ አልዌሮ ግድብ ነው፡፡

በኢትዮጵያ በተበጣጠሱ ማሳዎች ላይ የሚመረተው የምግብ ሰብል 80 በመቶው ለአምራቾቹ ፍጆታ ብቻ የሚውል ሲሆን ቀሪው 20 በመቶ ብቻ ለገበያ እንደሚቀርብ መረጃዎች ይጠቁማሉ፡፡ ሰፋፊ እርሻዎች የሚያመርቱት ምርት ድርሻ ከአጠቃላይ ሀገራዊ ምርቱ አምስት በመቶ ብቻ ነው፡፡ አሁን መንግስት ሁለት ምርጫዎች ያሉት ይመስላል፡ አንድም የእስካሁን አፈፃፀሙን ገምግሞና አሰራሩን አስተካክሎ አነስተኛ መጠን ያላቸውን መሬቶች መስጠቱን ሊቀጥል ይችላል፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ የሀገር ውስጥ ባለሃብቶች አቅም እስኪዳብር ድረስ ለም መሬትን ለውጭ ባለሃብቶች መስጠት ጭራሹን ሊያቆም ይችላል፡፡ ወደ ስራ መግባት ባልቻሉት ኢንቨስተሮች ላይ ደግሞ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እንደጀመረው ውል የመሰረዝና መሬቱን የማስመለስ ጥረቱን አጠናክሮ መቀጠሉ አይቀርም፡፡ ስኬታማነታቸው እየተነገረላቸው ያሉት እንደ ሳዑዲ ስታር ዓይነቶቹ ግን ትርፍ ማፈሳቸውን ይቀጥላሉ፡፡

 

Source: Wazema Radio 

The post ኢህአዴግ ላልተወሰነ ጊዜ መሬት እደላ ማቆሙና አላሙዲን | የዋዜማ ራድዮ ዜና ትንታኔ appeared first on Zehabesha Amharic.

ለተቃውሞ የተዘጉት ከሁመራ ወደ ጎንደር ፣ ከሰረቋ አርማጭሆ የሚወስዱት መንገዶች በሃገር ሽማግሌዎች ጣልቃ ገብነት ተከፈቱ

$
0
0

የሚሊዮኖች ድምጽ እንደዘገበው ከሁመራ በቅርብ እርቀት የምትገኘው በአከር ከተማ በደረሰን መረጃ ሕዝቡ በጉልበት አታስገድዱን እኛ ጎንደሬወች ነን በማለት ከሕወሃት ጋር ከትላንት ማምሻዉን ጀምሮ እንደተፋጠጡ ዘገባዎች ይጠቁማሉ። በአዲ ጎሹ በኩል ከትግራይ ወደ ወልቃይት የሚያስገባው አውራ ጎዳና እና እንዲሁም በተጨማሪ በዳንሻ በኩል ከሁመራ ወደ ጎንደር ፣ ከሰረቋ አርማጭሆ የሚወስዱት መንገዶች በሕዝቡ እስከ ትላንት ማምሻዉን ድረስ ተዘግተው ነበር።

gonder

ከአካባቢው የደረሰ መረጃ እንደሚጠቁመው በአገር ሽማግሌዎች ጣልቃ ገብነት ለጊዜው ከጎንደር ወደ ዳንሻ የሚወስደው መንገድ የተከፈተ ሲሆን፣ ይህ ከሽማግሌዎች ጋር የተደረገው መግባባት፣ ሕወሃቶች አፍነው የወሰዷቸውን የወልቃይት ማንነት ኮሚቴ አባላትን እንደሚለቁ ቃል ገብተው ሊሆን እንደሚችል ይገመታል። ሆኖም ህወሃት በሕዝቡ ላይ የከፈተው የሽብር ተግባራት ካላቆመና ያሰራቸውን አያፈናቸው በአስቸኳይ ካልፈታ፣ በሽማግሌውች ተማጽኖ ለጊዜው የተከፈተው መንገድ ብቻ ሳይሆን ሌሎችም በስፋት በማንኛው ጊዜ እንደገና ሊዘጉ እንደሚችሉ፣ ለአካባቢው ቅርበት ያላቸው የፖለቲክ ተንታኝ ይናገራሉ።

በወልቃይት ጠገዴ የተነሳው ተቃዉሞ፣ ሕወሃት የሕዝቡን ጥያቄ በማክበር በሰላም ካልፈታው፣ ወደ አልተፈለገ የለየለት የዘር ጦርነት እንደሚያመራና ከወልቃይት ጠገዴም አልፎም በቀላሉ ተቃዉሞው በሁሉም የአማራው ክልል ቦታዎች ሊዛመት እንደሚችል ያስጠነቅቃሉ።

የዳንሻ ጎንደር መንገድ በሽማግሌዎች ተማጽኖ ቢከፈተም፣ የሰሮቋ አርማጭሆ መንገድ ግን እስከዚህች ደቂቃ ድረስ በሺ በሚቆጠሩ ገበሬዎች አማካኝነት እንደተዘጋ ነው!!

The post ለተቃውሞ የተዘጉት ከሁመራ ወደ ጎንደር ፣ ከሰረቋ አርማጭሆ የሚወስዱት መንገዶች በሃገር ሽማግሌዎች ጣልቃ ገብነት ተከፈቱ appeared first on Zehabesha Amharic.

በደቡብ ኦሞ ዞን በኢንቨስትመንትና በስኳር ልማት ፕሮጄክት ስም የሚፈጸመው ሙስናና የሃብት ዘረፋ መረን የለቀቀ ነው

$
0
0

በልሁ ማንከልክሎት (ክፍል ሁለት)

  1. በኢንቨስትመንት ስም በሚደረገው የመሬት ቅርምት የወ/ሮ አዜብ መስፍን እጅ እንዳለበት ተገለጸ፤
  2. በመሬት ቅርምቱ አንድ መሬት/ቦታ ለተለያዩ ‹የሃሰት ኢንቨስተሮች › ተደጋግሞ እየተሰጠ ነው፤
  3. ህወኃቶች የዞኑን መሬት በመቀራመት ብቻ የሚዘርፉት የአገር ሃብት ከ930 ሚሊዮን ብር በላይ ይደርሳል፤
  4. በስኳር ልማቱ ፕሮጄክት በተለያዩ የሥልጣን ቦታዎች የህወኃት አባላት ተሰግስገዋል፤
  5. በስኳር ልማቱ ፕሮጄክት የሃሰት ሪፖርት እንዲያቀርቡ የተገደዱ ሠራተኞች እየለቀቁና እየተባረሩ ነው፤
  6. ደቡብ ኦሞ ዞን እኩይ ተልዕኮ ባለው ሰፈራ ስም የግጭት ቀጠና ሥጋት ተጋርጦባታል፡፡

ባለፈው ሣምንት በደቡብ ኦሞ ዞን የህወኃት አባላትና ደጋፊዎች በኢንቨስትመንት ሥም የሚፈጸመውን የመሬት ቅርምት በሚመለከት በዞኑ የተለያዩ ሴክተር መስሪያ ቤቶች  ባለሙያዎች በተደረገው ጥናት ላይ የተመለከተውን መረጃ ትክክለኛነት ያረጋገጡ ወገኖች ከ2006  በኋላ የተፈጸመውና የተገኘው መረጃ ደግሞ በእጅጉ የሚያስገርም ዓይን ያወጣ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ በዚህ ተጨማሪ መረጃ መሰረት 5 490 ሄክታር መሬት ‹ባለቤት› የኦሞ ሸለቆ አግሮ ኢንዱስትሪ የበላይ ጠባቂ ወ/ሮ አዜብ መሥፍን መሆናቸው፣ እንዲሁም ሳትኮን 16 500 ሄክታር መሬት ከተረከበና በመሬቱ ሥም ብድር ከወሰደ በኋላ መሬቱ ላይ አንዳችም ሥራ ሳይሰራ በመተው መሬቱ ለሌሎች ሰዎች መከፋፈሉን ፣…. የተገኙት ተጨማሪ መረጃዎች ያስረዳሉ፡፡ እነዚህ ወገኖች የወ/ሮ አዜብ መስፍን እጅ እስከ ደቡብ ኦሞ መድረሱና የ፣ሳትኮን› ድርጊት በእጅጉ እንዳስገረማቸውና ህወኃት በአባላቱና ደጋፊዎቹ በአገሪቱ ሃብት ላይ የሚፈጽመውን ዘረፋ በግልጽ የሚያሳይ ተጨባጭ ማስረጃ  በመሆኑ ጉዳዩ የሚመለከታቸው ትኩረት ሰጥተው እንዲከታተሉ ያስፈልጋል ሲሉ አሳስበዋል፡፡

12801147_966036103443554_4958790932868175941_n

በሌላ በኩል የዞኑ ተወላጅ አልሚዎች /ኢንቨስተሮች ላይ የሚፈጸመው ደግሞ የዚህ ተቃራኒ መሆኑ እንዳሳዘናቸው አልሸሸጉም፡፡ ይህም በዞኑ ነዋሪዎች የሚደረገው በመሬት ላይ የሚታይ ተግባራዊ የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴ በሴክተር መ/ቤቶች የአዋጭነት፣ የአካባቢያዊ  እና የማኅበራዊ ተጽዕኖ ተስማሚነት በባለሙያ ጥናት ተረጋግጦ የተሰጠ የባለሙያ ምስክርነትና ድጋፍ ዋጋ ተነፍጎት  የባንክ ብድር ያልተፈቀደላቸው ሲሆን በተቃራኒው አየር በአየር አንዳች ነገር ላልሰሩት የህወኃት አባላት እንደሚሰጣቸው ፣እነዚህ የጊዜው ሰዎች  የጂንካ ባንኮች ሲያነገራግሩ በቀጥታ ወላይታ ወደሚገኙ ባንኮች እንደሚሄዱና በቀላሉ ብድሩን እንደሚቀበሉ በተጨባጭ ማስረጃዎች የተረጋገጠ መሆኑን  ባለሙያዎች ያስረዳሉ ፡፡ ለዚህ ማስረጃነትም የዞኑ አግባብ ያላቸው መ/ቤቶች ባለሙያዎች ባካተተ ቡድን ጥናት ላይ ተመርኩዞ 156 ሄክታር ያለሙትና ቡና ያመረቱት  አቶ ተፈሪ ከበደ እና 300 ሄክታር ላይ ጥጥ አምርተው ለገበያ ያቀረበው ናሳ/አቶ ገበየሁ ምናሉ/ እርሻ ብድር ተከልክለው ሳትኮንን ጨምሮ እነ ‹እንቶኔ› ያለችግር አዲስ አበባ ተቀምጠው ብድር ማግኘታቸውን በማሳያነት አቅርበዋል፡፡

ከዚሁ ጋር በተያያዘ የዞኑ የግብርናና የኢንቨስትመንት ቢሮ ሠራተኞች በዞኑ አንድን ቦታ  ለተለያዩ ‹የሃሰት ኢንቨስተሮች› በመሰጠቱ የተሰጠው የኢንቨስትመንት መሬት ድምር በዞኑ ውስጥ ለዚህ ዓላማ ሊውል ከሚችለው ቦታ እንደሚበልጥ፣ ለዚህም ባለፈው ዓመት ለሎጅና ደን ቁጥጥር በሚል ለአንድ ‹የትግራይ ኢንቨስተር ›በበና ጸማ ወረዳ  የተሰጠውን በምድር ላይ የማይታይ  50 000 ሄክታር መሬት (ይህን በማሳየትም ለቦታ ዝግጅት/ምንጣሮ በሚል ብቻ ከባንክ  ብር 297 ሚሊዮን 500 ሺህ ሊጠየቅ እንደሚችል፣ይህም ህወኃቶች ከዞኑ የሚዘርፉትን ወደ ብር ከ930 ሚሊዮን ብር በላይ እንደሚያደርሰው )፣ እንዲሁም ምንም ሳይሰራበት ብድር ከተወሰደበት በኋላ  ለሌሎች የተከፋፈለውን የ‹ሳትኮን› 16 500 ሄክታር  በማስረጃነት ያቀርባሉ፡፡ ባለሙያዎቹ እንደሚያስረዱት  ከዞኑ ተወላጆች ውጪ ያሉት  የህወኃት ‹ኢንቨስተሮች› የኢንቨስትመንትና የንግድ  ፈቃድ ለማውጣትና መሬትና ብድር ለማግኘት የአካባቢው ማኅበረሰብ ቀርቶ የዞኑ ሴክተር መ/ቤት ባለሙያዎች እንዲያውቁት እንደማይደረግ…….  እና ከዞኑ አስተዳደር ከላይ በሚወርድ መመሪያ  የድጋፍና ትብብር ደብዳቤ እንደሚጻፍላቸው ፣ በባለፈው የባለሙያዎች ጥናት የለማ የተባለው ቦታም ለሠራተኞች ቀለብ በሚል በቆሎ ከመመረቱ ውጪ አንዳቸውም በፕሮጀክቱ ላይ የተገለጸውን የምርት ዓይነት (ጥጥ፣ ቡና፣ፓልም….) አንድም ሄክታር አልለማም፣ አንድ  ኩንታል አልተመረተም፡፡ ነገር ግን መሬቱን  ለምርት ለማዘጋጀት በሚል በቦታው ላይ ያለውን የግራር ዛፍ በመጨፍጨፍ ከሰል እንደሚያመርቱና ወደ አዲስ አበባ እንደሚጭኑ በዚህም የአካባቢው ደን እየተጨፈጨፈ መሆኑን ባለሙያዎች በመስክ ስራ ከህዝቡ ከሚቀርበው አቤቱታና በአይናቸው ከተመለከቱት እንደተረዱ ገልጸዋል፡፡ ከዚህም በመነሳት ባለሙያዎቹ የህወኃት የሃሰት ኢንቨስተሮች ዓላማ ማልማትና ከልማቱ ጥቅም ማግኘት ሳይሆን የአካባቢውን ሃብት በማሳየት  አየር ባየር ብድር ከመሰብሰብ ያለፈ እንዳልሆነ በቁጭት ይገልጻሉ፤ ከዚህም አልፎ በነዚህ የህወሃት አባላት በሚቀርቡ ከላይ ጸድቀው በሚመጡ የኢንቨስትመንት ፕሮፖዛሎች መሰረታዊ የአዋጭ4ነትና ኢኮኖሚያዊ አስተዋጽኦ መስፈርቶችና  የጥናት ግብኣቶች አለመካተታቸው ላይ ጥያቄ በሚያቀርቡ ባለሙያዎች ላይ ከ ‹ታዛዦቹ የዞን ሰክተር መ/ቤቶችና አስተዳደሩ› ማስፈራሪያ እንደደረሰባቸው አክለው ገልጸዋል፡፡

በሌላ ወገን ያሉት የዞኑ ተወላጆች ግን ያለበቂ ድጋፍና ትብብር ያላቸውን አቅም በሟሟጠጥ  የተንቀሳቀሱ መሆኑን  በዚህም ከላይ በተጠቀሱት የለማውን 456 ሄክታር ጨምሮ  በዞኑ ከ950 ሄክታር በላይ አልምተው ( አቶ ሁሴን 150 ሄክታር ፣ አቶ አሸናፊ ግርማ 50 ሄክታር፣ አቶ ሙስጠፋ 100 ሄክታር፣ አቶ አህመድ 36 ሄክታር፣ ሱዳሜል 162 ) ቡና፣ ጥጥ፣ ሰሊጥና ሌሎች ሰብሎችን አምርተው ለገበያ ማቅረባቸውን ይህም በግልጽ   ከሴክተር መ/ቤቶችና አስተዳደሩ አልፎ በአካባቢው ነዋሪዎች የሚታወቅ መሆኑንና ከዚህ ልማትም በፕሮጄክቱ አካባቢ የሚገኙ ነዋሪዎች በቀጥታና ተዘዋዋሪ ጥቅም እያገኙ መሆኑን አስረድተዋል ፡፡

እነዚህ‹‹ ስለዞናችንና አገራችን ከእንግዲህ ዝም አንልም›› የሚሉ በየሴክተር መ/ቤቶች ያሉ ባለሙያዎች በብሄራዊ ደረጃ በተጀመረው የስኳር ማምረት ስም ከረጅም ጊዜ ጀምሮ በስኳር ፕሮጄክቱ እርሻ ዙሪያ የሚገኙትን የሱርማ፣ የሙርሲ እና ቦዲ ብሄረሰቦች ህይወት ለችግር መጋለጡን፣ በቀጣይም  የ- ኛንጋቶም፣ዳሰነች፣ ካራ ፣ሃመር ብሄረሰቦች ህይወትም ለአደጋ እንደሚጋለጥ ግልጽ መሆኑን በጥናታቸው ጠቅሰዋል፡፡ ከዚህ ጋር በተያያዘ የአካባቢው ነዋሪዎችና  ከመንግስት ታጣቂ ኃይሎች ጋር ለተደጋጋሚ ግጭት መዳረጋቸውንና የውጪ ዜጎችን ጨምሮ ለሳላ ማጎ ወረዳ  የመንግስት ሰራተኞችና ነዋሪዎች እንዲሁም ለፕሮጄክቱ ሠራተኞችና ወደዚያ ለስራ የሚሄዱ ዜጎች ህይወት መቀጠፍና አካል መጉደል ምክንያት እንደሆነ ገልጸዋል፡፡

በመጨረሻም በዚህ ፕሮጀክት ውስጥ የሚደረገውን ሙስናን የሚደግፍ  ህገወጥ አሰራር፣ የህወኃት አባላት መሰግሰግና የሚቀርበውን የሃሰት ሪፖርት በሚመለከት እንዲሁም እኩይ ተልዕኮ አንግቦ በሚከናወነው ሰፈራ በዞኑ ያንዣበበውን የግጭት ሥጋት በሚመለከት በቀጣይ ክፍሎች በተከታታይ እንደሚያቀርቡ ቃል ገብተው፤አገር ወዳድ ኢትዮጵያዊያንና ሚዲያዎች ሁሉ እነዚህን የጥናት ሪፖርቶች ለኢትዮጵያዊያን እንዲያሰራጩ፣ በመተርጎም ለዓለም አቀፍ የአካባቢ ውድመትና የሰብዐዊ መብት ተከራካሪ ተቋማት እንዲያደርሱ  ጥሪ አቅርበዋል፡፡

The post በደቡብ ኦሞ ዞን በኢንቨስትመንትና በስኳር ልማት ፕሮጄክት ስም የሚፈጸመው ሙስናና የሃብት ዘረፋ መረን የለቀቀ ነው appeared first on Zehabesha Amharic.

ሕወሓት ራሱ በፈጠረው የጎሳ ፖለቲካ ውጤት ዲቃላውን ብኣዴንን እየወነጀለ ነው –ሰሜን ጎንደር ውጥረቱ ከሯል

$
0
0

gonder 2‪‎ምንሊክ ሳልሳዊ‬

ሕዝባዊ ወያኔ ሃርነት ትግራይ ብሎ ራሱን የሚጠራው እና ታላቋን ትግራይ በመስፋፋት ካልመሰረትኩ ነጻ አውጪ የሚለውን ስሜን አልቀይርም በማለት በአማራ እና በአፋር ክልሎች የመስፋፋት እቅዱን ለመተግበር ሲሮጥ ከፍተኛ የሆነ እንቅፋት ከአማራው ሕዝብ ስለተጋረደበት ራሱ የፈጠረውን ዲቃላውን ኢሕዴን/ብኣዴንን መወንጀል መጀመሩ ከሕወሓት የገደል ማሚቱዎች የተገኙ መረጃዎች እየጠቆሙ ነው::ሕወሓት ፊቱን ወደ ተላላኪዎቹ አዙሩ በምትካቸው ከሕወሓት ጉያ የተመለመሉ አማርኛ ተናጋሪ ሕወሓቶችን ለመተካት እየሮጠ ይገኛል::በሰሜን ጎንደር ተፈጥሮ የሚገኘው ከፍተኛ የሆነ የሕዝብ አመጽ ወደ ግጭት የተቀየር ሲሆን ከጎንደር ከተማ ጀምሮ እስከ ዳንሻ ድረስ ሕዝቡ አስፈላጊውን የሕይወት መስዋትነት ለመክፈል ጥርሱን ነክሶ መሰሳቱ ታይቷል::

የሕወሓት የገደል ማሚቱዎች በጋራ እና በፍቅር የኖረን ሕዝብ በመለያየት ለማናከስ ያደረጉት የፕሮፓጋንዳ ዘመቻ መክሸፉን ካረጋገጡ በኋላ ብኣዴን የሚሉትን ድርጅት ማእከሉን አፍርሰው ዳግም ለመስራት ማቀዳቸው ታውቋል::ሕወሓቶች ብኣዴንን አፍርሰው ለመስራት ያቀዱት በአሁን ሰአት የያዙትን የግዛት ማስፋፋት እያደናቀፈብን ያለው ብኣዴን ነው ከሚል ድምዳሜ ላይ መድረሳቸው መሆኑ ታውቋል::ብኣዴን የቀድሞ አጼዎችን ስርኣት ዳግም ለመመለስ የሚለው የሕወሓት ኋላ ቀር እና ራስን ከሞቱ ስርኣቶች ጋር የማወዳደር ሱስ በያዝነው የሰለጠነ 21ኛው ክፍለዘመን ላይ አገርሽቶበታል::

gonder

ሕወሓት በዘር ጥላቻ የተሞሉ ካድሬዎቹን ቅርሻት ሲተፋ ያላወቀው ነገር ቢኖር የሕወሓትን የመስፋፋት ፖሊሲ ያማረረው የጠላው ሕዝቡ እንጂ ብኣዴን አለመሆኑን ነው::አሁን በስልጣን ላይ ያሉ የብኣዴን አመራሮችን ማርኛ ተናጋሪ በሆኑ የሕወሓት ካድሬዎች ለመተካት እና ካሰበው የመስፋፋት እቅድ ለመድረስ ብኣዴንን መወንጀሉ ሊያስደንቅ አይገባም ሲሉ የብኣዴን ሰዎች ይናገራሉ::የሕወሓት የግዛት የመስፋፋት እና ታላቋን ትግራይ የመፍጠር ሕልም እየተደናቀፈ ሲሆን የትግራይ ሕዝብ በራሱ የሕወሓትን አካሄድ እንደማይደግፈው ከአረና ፓርቲ አከባቢ የሚገኙ መረጃዎች ይጠቁማሉ::ሕወሓት በኢትዮጵያ ላይ የሚከተለው የጎሳ ፖለቲካ ከፍተኛ የሆነ አደጋ ጋርጦበታል::እንዲሁም በተጨማሪ የሕወሓትን አካሄድ ከከተማ እስከ ገጠር ያለው ሕዝብ ስለነቃበት ተቃውሞውን እያሰማበት ይገኛል::

The post ሕወሓት ራሱ በፈጠረው የጎሳ ፖለቲካ ውጤት ዲቃላውን ብኣዴንን እየወነጀለ ነው – ሰሜን ጎንደር ውጥረቱ ከሯል appeared first on Zehabesha Amharic.

በባህርዳር የደጋ እስጢፋኖስ ገዳም በጀልባ ጠመንጃ በታጠቁ ኃይሎች ተከበበ

$
0
0
  • በአመክሮ ላይ ካሉ ጥቁር ራሶች ጋር ውዝግብ በመፍጠር ደብድበዋቸዋል
  • የደሴቶቹና የአካባቢው ኅብረተሰብ ኹኔታውን በንቃት እየተከታተሉ ናቸው
  • የ740 ዓመት ገዳሙ፣ የበርካታ ጥንታውያን ብራናዎችና ቅርሶች ማዕከል ነው

ሐራ ተዋሕዶ እንደዘገበው

በባሕር ዳር ሀገረ ስብከት በጣና ሐይቅ ውስጥ ከሚገኙ የደሴት ገዳማት አንዱ የኾነው ጥንታዊው የዳጋ እስጢፋኖስ ገዳም፣ ካለፈው ሳምንት ኀሙስ ጀምሮ ማንነታቸው ባልታወቁ ታጣቂዎች የዘረፋ ስጋት ተደቅኖበት እንደሚገኝ ተገለጸ፡፡

dega estifanos

ምንጮች እንደገለጹት፣ ባለፈው ኃሙስ ምሽት ግለሰቦቹ በሦስት ጀልባዎች ከፎገራ አቅጣጫ በመምጣት ወደ ገዳሙ የደሴት ክልል ተጠግተው ያደሩ ሲኾን፤ ትላንት፣ መጋቢት 12 ቀን ምሽት 2 ሰዓት ላይ ደግሞ ጀልባዎቹ በቁጥር ጨምረውና ግለሰቦቹም በትጥቅ ተደግፈው መምጣታቸው ስጋቱን ከፍ አድርጎታል፡፡

ኀሙስ ምሽት የመጡት ጀልባዎች ዓርብ ጠዋት ስፍራውን ለቀው ቢሔዱም ትላንት ምሽት ከተመሳሳይ አቅጣጫ በስምንት ጀልባዎች ተጓጉዘው የመጡት የታጠቁ ግለሰቦች በገዳሙ አቅራቢያ ማደራቸው በምንጮቹ ተጠቅሷል፡፡ ይህ ዜና እስከተጠናቀረበት ዛሬ ጠዋት ድረስም፣ ከስምንቱ ጀልባዎች አምስቱ ከነታጣቂዎቹ በስፍራው እንዳሉ ተገልጧል፡፡

አመጣጣቸው ዓሣ ለማስገር እንደኾነ በመግለጽ ኃሙስ ሌሊቱን ከገዳሙ አበምኔትና ከማኅበረ መነኰሳቱ ጋር ፍጥጫ ውስጥ ገብተው ያደሩት ግለሰቦቹ፤ ዓርብ ጠዋት በአመክሮ ላይ ከሚገኙ ጥቁር ራሶች አንዱን በመደብደብ ጉዳት ማድረሳቸው ታውቋል፡፡

“የአካባቢው ነዋሪዎች እንኳ፣ ዓሣ እዚያ የማውጣት ልምድ የላቸውም፤”  ይላሉ ምንጮቹ፡፡ ስለግለሰቦቹ አመጣጥ ሲያስረዱም፥ ወቅቱ የጾም ወራት በመኾኑና ማኅበረ መነኮሳቱም ሱባኤ ላይ በመኾናቸው አጋጣሚውን ተጠቅሞ ዘረፋ ለማካሔድ የሚደረግ ሙከራ እንጂ ሌላ ሊኾን እንደማይችል ይናገራሉ፡፡

ካለፈው ኃሙስ ምሽት ጀምሮ የገዳሙ ማኅበረ መነኮሳት ከሌሎች የደሴታቱ ገዳማት፣ በዙሪያውና ባሻገሩ ከሚኖረው ማኅበረሰብ ጋር በመደዋወል አካባቢውን በንቃት እየጠበቁ ቢኾንም የክልሉ መንግሥት የግለሰቦቹን ማንነት በመለየትና በመቆጣጠር አስቸኳይ ጸጥታዊ ድጋፍ እንዲያደርግላቸው ጠይቀዋል፡፡

ከዚኽ ቀደም የመነኮሳቱን አልባሳት በመልበስና ተመሳስሎ በመግባት ጭምር በገዳሙ ዕድሜ ጠገብና ውድ ቅርሶች ላይ ተደጋጋሚ የዘረፋ ሙከራዎች መደረጋቸውን ምንጮቹ አስታውሰው፤ ገዳማውያኑና የአካባቢው ማኅበረሰብ በንቃት መከታተላቸውን አጠናክረው እንዲቀጥሉ አሳስበዋል፤ መረጃው የደረሰው የክልሉ መንግሥትም አስፈላጊውን ክትትል በማድረግ የተጠየቀውን ድጋፍ በአፋጣኝ እንዲሰጥ ጠይቀዋል፡፡

ከአትክልት ልማት ምንጣሮ ጋር በተያያዘ ባለፈው ዓመት ጥር ወር በገዳሙ ተቀስቅሶ የነበረው የእሳት ቃጠሎ፤ በደሴያቱ ማኅበረ መነኮሳት፣ በአቅራቢያው ነዋሪዎች፣ ከባሕር ዳር ከተማ በጀልባ ተጓጉዘው በደረሱ አገልጋዮችና ምእመናን፣ በክልሉ መስተዳድር ሓላፊዎችና በጸጥታ ኃይሎች የጋራ ርብርብ ከቤተ ክርስቲያኑ መቶ ሜትር ባነሰ ርቀት ላይ መጥፋቱ ይታወሳል፡፡
09 Tana Lake-D.Estifanos 19
ከ740 ዓመታት በላይ ያስቆጠረው ጥንታዊው የዳጋ እስጢፋኖስ ገዳም፣ በሐይቁ የደቡብ ምሥራቅ ገጽ ከባሕር ዳር ከተማ የኹለት ሰዓት የጀልባ ጉዞ ርቀት ላይ ይገኛል፡፡ ለዘመናት የተካበቱ አያሌ የብራና መጻሕፍትና ንዋያተ ቅድሳት ማእከል ከመኾኑም በላይ፤ በዐፄ ዘርዓ ያዕቆብ ዘመን የተሣለች ምስለ ፍቁር ወልዳ ሥዕል፣ የመሥራቹ የአቡነ ኂሩተ አምላክ መቋሚያ፤ የታወቁት ነገሥታት የዐፄ ዳዊት፣ የዐፄ ዘርዓ ያዕቆብ፣ የዐፄ ሱስንዮስ፣ የዐፄ ፋሲልና የሌሎችም ነገሥታት አዕፅምት፣ የወግና የክብር ዕቃዎች/ዘውዶች፣ አልባሳት፣ ጎራዴ …/ ተጠብቀው ይገኙበታል፡፡

የገዳሙ መነኮሳት የሚመገቡት ከዳጉሳ እህል የተዘጋጀ ዳቤ የሚመስል መኩሬታ የሚባል ምግብ ነው፤ መተዳደርያቸውም አትክልትና ፍራፍሬ በማልማት ሲኾን ሙዝ፣ ሸንኮራ፣ ሎሚ፣ ትርንጎ፣ ፓፓያ፣ ማሽላ ያመርታሉ፡፡

The post በባህርዳር የደጋ እስጢፋኖስ ገዳም በጀልባ ጠመንጃ በታጠቁ ኃይሎች ተከበበ appeared first on Zehabesha Amharic.

የመንግስቱ ኃይለማርያም አዲስ መጽሐፍ ፃፉ –“ኢሳያስ አፈወርቂ የተወለደው ትግራይ ነው.. ያሳደጉት የወሎው አገረ ገዢ ናቸው”አሉ

$
0
0

mengistu

(ዘ-ሐበሻ) የቀድሞው የኢትዮጵያ ወታደራዊ አስተዳደር ፕሬዚዳንት መንግስቱ ኃይለማርያም ‘ትግላችን’ የተሰኘውን 2ኛውን ቅጽ መጽሐፋቸውን ጽፈው ለንባብ አበቁ::

ትግላችን የተሰኘው የኮለኔሉ መጽሐፍ በጸሃይ አሳታሚነት የመጀመሪያው ዕትም ወጥቶ ነበር:: ሆኖም ግን መንግስቱ ኃይለማርያምን የሚቃወሙ ድረገጾች መጽሐፉን በስካነር ኮፒ በማድረግ በነፃ ሕዝብ ጋር እንዲዳረስ በማድረጋቸው አሳታሚው ከፍተና ኪሳራ ላይ ወድቆ እንደበር ይታወሳል:: ኮለኔሉ መጽሐፉን ጽፈው ለአሳታሚው ሲያስረክቡ ገንዘባቸውን የተቀበሉ በመሆኑ ምንም ዓይነት ኪሳራ ባይደርስባቸውም ጸሐይ አሳታሚ ድርጅት ግን ክፍል 2ቱን መጽሐፍ ለማሳተም አልደፈረም ሲሉ የዘ-ሐበሻ ምንጮች ይገልጻሉ::

አዲሱ የኮለኔል መንግስቱ መጽሐፍ በዓይናለም አሳታሚ ድርጅት አማካኝነት የወጣ ሲሆን አሁንም በመንግስቱ ኃይለማርያም ላይ ጥላቻና ተቃውሞ ያላቸው ሰዎች መጽሀፉን በስካን አድረገው በነጻ በየኢንተርኔቱ ይለቁታል የሚለው ስጋት አለ::

ኮ/ል መንግስቱ በቁጥር ሁለት መጽሐፋቸው ” ብርጋዴር ጀነራል ተፈሪ በንቲን የደርጉ ሊቀመንበር ማድረግና ብርጋዴር ጀነራል ጌታቸው ናደውን በቅድሚያ፣ የምድር ጦር አዛዥ በኋላም የኤርትራ ክፍለ ሀገር አስተዳዳሪና የመላው የሰሜን መለዮ ለባሽ ሠራዊት አዛዥ በማድረግ ረገድ የተሰራው ስህተት የማንም ሳይሆን የእኔ ነበር” ሲሉ በጀርባው ሽፋን ላይ ጽፈዋል::

mengistu hailemariam Tiglachin

መንግስቱ ኃይለማርያም በአዲሱ መጽሐፋቸው ስለ ኢሳያስ አፈወርቂም ተናግረዋል:: “ዛሬ የሻዕቢያ መሪ የሆነው ኢሳይያስ አፈወርቂ ኤርትራ ይወለድ እንጂ አባቱም እናቱም የትግራይ ተወላጆች ሲሆኑ እሱን ያሳደጉትና ያስተማሩት ደግሞ የወሎ ክፍለ ሀገር እንደራሴ የነበሩት እና የታወቁት ኢትዮጵያዊ አጎቱ ደጃዝማች ሰለሞን አብርሓ በደሴ ከተማ ነው” ሲሉ መንግስቱ ኤርትራ ከኢትዮጵያ ጋር በፌዴሬሽን ከተቀላቀለች በኋላ ኢየሩሳሌም ባለው የኢትዮጵያ ገዳም ተመድበው የነበሩት አቡነ ፊሊጶስን ጠቅሰው ጽፈዋል፡፡

መጽሐፉ በኢትዮጵያ በገበያ ላይ የዋለ ሲሆን በአሜሪካ እና በውጩ ዓለም እንዴት እንደሚደረስ ዘ-ሐበሻ የደረሳት መረጃ የለም::

The post የመንግስቱ ኃይለማርያም አዲስ መጽሐፍ ፃፉ – “ኢሳያስ አፈወርቂ የተወለደው ትግራይ ነው.. ያሳደጉት የወሎው አገረ ገዢ ናቸው” አሉ appeared first on Zehabesha Amharic.


የትግራይ አስተዳዳሪው የጎንደሩ ንጉስ ትምክህተኛው አባይ ወልዱ የሕውሓት ሊቀ መንበር

$
0
0
ትምክህተኛው አባይ ወልዱ የሕውሓት ሊቀ መንበር ።

ትምክህተኛው አባይ ወልዱ የሕውሓት ሊቀ መንበር ።

በእሱ በሚመራው ሕውሓት በእሱ በሚታዘዘው የአፋኝ ቡድን አማሮችን ይገድላሉ ።
ሕዝብን ዘር ማጥፋት ይቅርና አጠፋለሁ ብሎ መሞከር ታላቅ ሰብዓዊ ወንጀል ነው ለሂትለር አልበጀውም
-ከታሪክ እንደተረዳነው የሁለተኛው የዓለም ጦርነት መገባደጃ ላይ የጀርመን ከተሞች በሕብረ ብሔሩ ጦር ሲያዙ ።
ጥጋበኛው ሂትለር ልጆቹንና ሚስቱን ከገደላቸው በኋላ ቤቱን አቃጥሎ እራሱንና ቤተ ሰቦቹም ጭምር በእሳት አረው ወደ አመድነት ተቀይረዋል ።
እሱ በሥራው ነበር ግን ከባዱን ዋጋ የከፈሉት የጀርመን ወይዛዝርት የከፈሉት ዋጋ ለመላው የጀርመን ሕዝብ ጠባሳው የማይጠፋ ቅስም የሚሰብር ነበር ሴቶች ለጅምላ ወንዶች ተደፍረዋል እንደሰው ሳይሆን ተራ መጫወቻ ነበር የሆኑት ትዕቢት ና ትምክህት የመጨረሻውን ውጤት አይተነዋል ኃይል ከእግዚአብሔር መሆኑን እናምናለን ።
እንዲሞት የፈረድክበት ሕዝብ አንተን ቢገጥምህ ምክንያት አለው ።
አንተ ግን ከአማራ ሕዝብ ነፍሳቸውን ለመቀማት የመጣኸው ምንም ምክንያት የለህም ።
እባክህ ንጉሥ ሆይ ሥልጣንህ በመቀሌ እንደሆነች ትቅር ከተከዜ ማዶ የቋመጥክበት የጎንደር ምድር ጤናም አይሆንህም ።
የጎንደር ሕዝብ ወሎን ሸዋን ጎጃምን ይዞ አርበኞት አንተን ለመዋጋት ለመቶ ዓመት ቢሆንም ቀለብና ስንቅ አይቸግራቸውም ጦርነቱን ጀምረው በመጀመሪያ የውስጥ ሰላዮችህ ከአማራ ምድር ተጠርገው ይወጣሉ ከዛ በኋላ አርበኞች በቀን በየዘመድ ቤቱ ይውላሉ ፀሀይ አይመታቸውም ይህ ቅጥረኛው ብአዴንና አማረኛ ተናጋሪው ትግሬ የአማራ ምድር አትታገሳቸውም ሁሉም ይወጣሉ።
አሁን እያየን ነው በኦሮሞ ምድር 111 ቁጥር አስቀድመው ወጠዋል ነገም ከአማራ የሚሆነው ይህ ነው ።
ክቡር ንጉሥ ሆይ የሚመጣው ጥፋት በዙፋንህ ስትል አስቁመው በሰላም ለዘመናት አብረን እነደኖርነው አሁንም በሰላም ከትግራይ ሕዝብ ጋር አብረን እንኑር ።
ምንም አብሮ የመኖሩን እሴቶች ጨርሳችሁ ብትቆርጡትም ከዚህ ላይ ብታቆሙት የብዙኃን ደም ሳይፈስ እንደጭራ የመነመነች አብሮ መኖር ተስፋ ጨርሳ አልሞተችም እንደገና ትለመልማለች ።

ዘለቀ በላይነህ

The post የትግራይ አስተዳዳሪው የጎንደሩ ንጉስ ትምክህተኛው አባይ ወልዱ የሕውሓት ሊቀ መንበር appeared first on Zehabesha Amharic.

የ 100% ምርጫ አቀናባሪ በሰብዓዊ መብት ዙሪያ ሪፖርት ያቀርባሉ –የሚሊዮኖች ድምጽ

$
0
0

1930786_981723211912613_3887250359965847240_nዶር አዲሱ ገብረ እግዚአብሄርን መቼም የማያውቅ አለ ብለን አናምንም። በተለይም የኢትዮጵያን ፖለቲካ የሚከታተል። የሕወሃት አባል ናቸው። በምርጫ ዘጠና ሰባት ወቅት ኢሕአዴግን ወክለው ተወዳድረው ነበር። ከዚያም የብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ዋና ጸሃፊ ሆነው አገልግለዋል። የምርጫ ቦርድ ሰብሳቢው ፕሮፌሰር (የእንሳሳ ሐኪሙ) መርጋ የነበሩ ቢሆንም፣ ፕሮፌሰሩ ለይስሙላ የተቀመጡና የሚሰጣቸውን መመሪያ የሚያነቡ እንጂ ፣ በቦርዱ ፈላጭ ቆራጭ የነበሩት ዶር አዲሱ ነበሩ።

በአገሪቷ በሁሉም ክልሎች ጠንካራ መዋቅር የነበረው የአንድነት ፓርቲ እንደነበረ የሚታወስ ነው። አንድነት የምርጫ ዘመቻ ከመጀመሩ በፊት በ34 ዞኖች ጽ/ቤቶች ከፍቶ 547 መቀመጫ ላለው ፓርላማ ከአምስት መቶ በላይ ተወዳዳሪዎችን አዘጋጅቶ የጨረስ ደርጅት ነበር።

በሕወሃት፣ አንድነት ፓርቲ ከጨዋታ ዉጭ እንዲሆን የፖለቲክ ዉሳኔ በመወሰኑ፣ ከሕወሃት በተሰጠ የፖለቲካ መመሪያ፣ በገንዘብ የተገዙና አስቀድሞ የሰረጉ ጥቂት ግለሰቦችን በማሰባሰብ ፣ ተለጣፊ የአንድነት አንጃ በመፍጠር፣ ሕገ ወጥ በሆነ መልኩ የአንድነት ፓርቲ ታግዷል። ይሄንን በቀዳሚነት ሲመሩና ሲያንቀሳቅሱ የነበሩት ዶር አዲሱ ነበሩ።

በዶር አዲሱ አመራር፣ የ2007 ምርጫ መቶ በመቶ የሚለውን አስቂኝ ድል፣ ምርጫ ቦርድ ለሕወሃት/ኢሕአዴግ አጎናጽፏል። ዶር አዲሱ ለተሰጣቸው የሕወሃት ተልእኮ ከሚጠበቀው በላይ ዉጤት ስላመጡም የሰብዓዊ መብት ኮሚሽን ሃላፊ ሆነው ተሾመዋል።

በፕሮፌሰር መስፍን ወልደማሪያም የተቋቋመው ዝነኛው የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ጉባኤ በኢትዮጵያ ላለፉት 4 ወራት በተነሱ ተቃዉሞውች ዙሪያ የተፈጸሙ ኢሰዓዊ የሰባአዊ መብት ረገጣዎች፣ ግድያዎችን፣ ድብደባዎችን፣ በመረጃዎች በማስደገፍ ይፋ አድርጓል።

በሕግ፣ ሃላፊነቱ የሰብአዊ መብት ጥሰት መከታተል የሆነውና ዝምታን መርጦ የነበረው በዶር አዲሱ የሚመራው የስብአዊ መብት ኮሚሽን፣ የኢሰመጉን ረፖርት ተከትሎ ፣ መመሪያ ተላልፎለት ይሁን በሌላ ምክንያት ብቅ እንዳለ እያየን ነው። ዶር አዲሱ የሚመሩት ኮሚሽን ለፓርላማ በቅርቡ ሪፖርት እንደሚያቀርብ፣ ዶር አዲሱ ራሳቸው ለሜዲያው ገልጸዋል። የዚህ ረፖርት ይዘት ምን እንደሚመስል ገና ባይታወቅም ከወዲሁ ሰዎች ያላቸውን ግመት እየሰጡ ነው።

“ዶር አዲሱ ሰዎች መገደላቸውን እና ጥፋት መድረሱን አምነው፣ የደረሰዉን ጉዳት ግን አሳንሰው ነው ያቀርባሉ። እነ ጌታቸው ረዳ ከተናገሩት የተለየ ነገር አይናገሩም” ያሉን አንድ ተንታኝ ለደረሱትም ጥፋት፣ ዶር አዲሱ ተጠያቂ ኦህድድን ሊያደረጉ እንደሚችሉ ይናገራሉ፣ በአሉታዊነት።

ሌላ ተንታኝ የተለየ አዎንታዊ አስተያየት ነው አላቸው። “እነ ኃይለማሪያም ያለዉን ችግር አውቀዋል። በዚህ መቀጠል እንደማይችሉ ገብቷቸዋል። መሰረታዊ ለዉጥ ለማምጣት ሳይፈለጉ አይቀርም። ኢሰመጉን፣ ሆነ ተቃዋሚዎች የሚሉትን መስማት፣ እዉነትም ቢሆን፣ ሽንፈት ስለሚመስላቸው እነ ኢሰመጉ ያቀረቡትን በተለየ መልክ ጠርዘው፣ በነዶር አዲሱ በኩል ፓርላማ ዉስጥ በማስቀረብ፣ የሕግ ስልጣን ያለውም ፓርላማ ለመጀመሪያ ጊዜ፣ መሰረታውዊ ዉሳኔዎችን እንዲወስን ለማድረግ ሳያስቡ አይቀርም” ሲሉ አስተያየት ይሠጣሉ።

ዶር አዲሱ ገብረ እግዚአብሄር ሕዝብን ሳይሆን ህወሃትን የሚያገለግሉ፣ ሕግን ሳይሆን የሕወሃት መመሪያን የሚከተሉ ሰው እንደሆኑ እናውቃለን። የመቶ በመቶ የምርጫ ዉጤት እና የርሳቸው አሳፋሪ ሥራን መለስ ብለው የማሰብ ብስለት ካላቸው ስማቸዉን ለማደስ ይሄን አጋጥሚ ሊጠቀሙበት ይችላሉ። በሌላ ጎኑ ግን ፣ እንደ ሌሎች፣ ግትርና ሁልጊዜ እኛ ብቻ ነን የምናውቀው እንደደሚሉት፣ የሕወሃት አመራሮች፣ ስህተታቸውን መረዳት የተሳናቸው ደካም ሰው ሆኖ መቀጠሉን ሊመርጡ ይችላሉ። በቅርቡ የምናየው ይሆናል።

The post የ 100% ምርጫ አቀናባሪ በሰብዓዊ መብት ዙሪያ ሪፖርት ያቀርባሉ – የሚሊዮኖች ድምጽ appeared first on Zehabesha Amharic.

ሰበር ዜና: በምዕራብ ወለጋ መንዲ ከተማ የገበያ ማዕከል እየነደደ ነው

$
0
0

Mendi

(ዘ-ሐበሻ) የኦሮሞ ሕዝብ ተቃውሞ በተለያዩ ከተሞች በቀጠለበት በአሁኑ ወቅት በምዕራብ ወለጋ መንዲ ከተማ ውስጥ አንድ የገበያ ማዕከል በእሳት እየነደደ መሆኑ ተሰማ::

በምዕራብ ወለጋ ዞን ውስጥ የምትገኘው መንዲ ከተማ በ2005 ዓ.ም በተደረገ ቆጠራ 18,020 ሰዎች ይኖሩባታል::

ይህ ዜና ለዘ-ሐበሻ በደረሰበት ሰዓት እየተቃጠለ የሚገኘው የገበያ ማዕከል ባለቤት የኦሮሞ ሕዝብን ንቅናቄ በገንዘብ ይደግፋሉ ተብለው በ በሥርዓቱ የተፈረጁ ግለሰብ ንብረት ነው የሚሉት አስተያየት ሰጪዎች ምናልባት እሳቱን ሆን ብለው ያስነሱት የስርዓቱ ተላላኪዎች ሳይሆኑ እንደማይቀሩ ያላቸውን አስተያየት ሰጥተዋል::

እየተቃጠለ በሚገኘው በዚሁ የመንዲው የገበያ ማዕከል እየጠፋ ያለው የንብረት መጠን ለጊዜው ባይታወቅም የአካባቢው ነዋሪ እሳቱን ለማጥፋት እየተረባረበ ይገኛል::

The post ሰበር ዜና: በምዕራብ ወለጋ መንዲ ከተማ የገበያ ማዕከል እየነደደ ነው appeared first on Zehabesha Amharic.

በኦሮሚያ ክልል የተነሳውን ተቃውሞ ተከትሎ የተወሰዱ የመብት ረገጣዎችን ያጋለጠው የሰብዓዊ መብት ሪፖርት ሲዳሰስ |ልዩ ጥንቅር

በመቶዎች የሚቆጠሩ ጋዜጣዊ መግለጫዎች –አንዱዓለም ተፈራ –የእስከመቼ አዘጋጅ

$
0
0

ማክሰኞ መጋቢት ፲፫ ቀን፣ ፳፻፰ ዓመተ ምህረት

eskemecheገዢው አምባገነን የትግሬዎች ነፃ አውጪ ግንባር መንግሥት በየዕለቱ በሚያደርገው ፀረ-ኢትዮጵያዊ ተግባር፤ የተለያዩ የፖለቲካ ሕዝባዊ ስብስቦች መግለጫ ያወጣሉ። አዳዲስና ነባር የፖለቲካ ድርጅቶች፤ አለን በማለት ስማቸውን በአንባቢዎች ያስመዘግባሉ። ለመሆኑ ጋዜጣዊ መገለጫዎች ለምንድን ጉዳይ ነው የሚወጡት? ማነው የሚያወጣቸው? መግለጫዎችን ተከትሎ የሚተገበሩት ምንድን ናቸው? አሉስ ወይ? መግለጫ አውጪዎቹና መግለጫ ያላወጡ የፖለቲካ ሕዝባዊ አካሎች መለያቸው ምንድን ነው? መግለጫዎችና አውጪዎቻቸው፤ ሕዝባዊ ናቸው ወይንስ ጠባብ ወገንተኛ? መልዕክት አላቸው ወይንስ አደረግሁ ለማለት የተወረወሩ? አስፈላጊነታቸውስ ምን ያህል ነው? በተደጋጋሚ ጋዜጣዊ መግለጫ በተንጎደጎዱ ወቅት የደረሱኝ እጦማሮች ነበሩ። ሁሉም ወቀሳዎች ናቸው። “ለምን መግለጫ አታወጣም?” “ካሁን በፊትም ዝም ብለሃል!” የሚሉና ሌሎችም ከጠላት ጋር ወግነሃል ያሉኝም ነበሩባቸው። ለምንድን ነው መግለጫ ማውጣት ያለብኝ? መግለጫ አላወጣም። ይሄን ግልጽ በሆነ መንገድ ማስቀመጥ አለብኝ።

መንግሥታትና ድርጅቶች መግለጫ ሲያወጡ፤ መሠረታዊ ዓላማው፤ ጉዳዩ ካተኮረባቸው አካላት ጋር ተባባሪ መሆናቸውን አንባቢ ወይንም አዳማጭ እንዲያውቅላቸው አይደለም። መግለጫውን የሚያወጡት፤ ነግ ለኔ ብለው፤ ካሁኑ ቀድሜ እርምጃ እወስዳለሁ ማለታቸው ነው። ከማንኛውም መግለጫ ጋር፤ አብሮ የሚሄድ መልዕክት አለ። “የሚያስፈልገውን ለማድረግ እንጥራለን!” “ከዛሬ ጀምሮ ይሄን ወይንም ያኛውን እናደርጋለን!” “በሚያስፈልገው ነገር ሁሉ ልንረዳችሁ ዝግጁ ነን!” “ሊረዷችሁ የሚችሉ ሰዎችን ልከንላችኋል!” “ለመቋቋሚያ እንዲያግዛችሁ ገንዘብ ልከንላችኋል!” እና የመሳሰሉት ናቸው። እንግዲህ ልብ ብለን ብናጤነው፤ ዋናው የመግለጫው ማሠሪያ፣ ይሄ ከወደኋላ የተከተለው ተግባር ነው። እስኪ ወደኛ፤ በተለይም የገዢውን ቡድን ተግባር የሚያወግዙትን ጋዜጣዊ መግለጫዎችና አውጪዎቻቸውን እንመለስ።

በጠላትን ፈርጀው የሚታጋሉትን ገዢ ቡድን፤ “ይሄን በማድረጉ አውግዘናል!” ማለት ምንድን ነው ትርጉሙ? ካወገዙስ በኋላ ምንድን አንው የተከተለው? “ድርጅታችን የበለጠ ትግሉን ይቀጥላል!” ማለትስ ምንድን ነው ትርጉሙ? “ያንን እስኪያደርግ ድረስ የበለጠ አልተጋልንም!” የሚል ኑዛዜ ነው? “የታሰሩትን እንዲፈታ እንጠይቃለን!” ማለት ለፌዝ ነው? “ከሌሎች ጋር እንተባበራለን!” የሚል ማስፈራሪያ አስቀምጦ ድምፅን ማጥፋትስ ለምን አስፈለገ? በተለይ የመተባበርን ጉዳይ አስመልክቶ፤ “እተባበራለሁ!” ያላለ ድርጅት የለም። ትግሉ “ያለአንድነት የትም አይደርስም!” ያላለ ድርጅት የለም። አስፈላጊነቱን ያላሰመረ፣ የሕዝቡ ጥያቄ መሆኑን ያላስገነዘበና ጥሪውን በተደጋጋሚ ያላወጀ ድርጅት የለም። ታዲያ አሁን የት ላይ ቆመናል? መግለጫዎቹ አደረግሁ ለማለት ነበር የወጡት? ለመተባበር ጥሪ ያደረገ ድርጅት፤ ከወዲሁ አብሮ የመሥራትን አስፈላጊነት ማመን ብቻ ሳይሆን፤ ለማስተባበርም ኃላፊነቱን መውሰዱ ነው። ታዲያ ያንን ኃላፊነት ለመውሰድ የወሰነ ድርጅት፤ ሌሎች ለሚጠሩት ትብብር ለምን መልስ መሥጠት ገደደው? ምን መልስ ሠጠ? እኔ ለጠራሁት ሌሎች መልስ ይሥጡ እንጂ፤ ሌሎች ለጠሩት እኔ መልስ አልሠጥም ማለት ይሆን? አስመሳይነት ማለት ምን ማለት ነው? ዋሾነት በምን ይከሰታል? በዚህ ጉንጉን የተተበተበ ሂደት ምን ያህል ካለበት ፎቀቅ ማለ ይቻላል?

እዚህ ላይ ነው የኔ መግለጫ አለማውጣት ትርጉም የሚሠጠው። የምደግፈው ተግባራዊ ጉልበት በማልሠጥበት ሂደት፤ መግለጫ አላወጣም። በርግጥ አንዳንድ ያደረግኋቸውን ለማመላከት፤ የእስላሞችን እንቅስቃሴ አስመልክቶ በግፍ መሪዎቻቸው ሲታሰሩ እኛም ሰለምን፤ በማለት ከትቤያለሁ። አብረሃ ደስታ ሲታሰር አሻንጉሊቶች ናችሁ በማለት ከትቤያለሁ። ሌሎችንም በዚሁ ማስታወሻ መድረኬ ጠቃቅሻለሁ። ዋናው ቁም ነገር ግን፤ የኢትዮጵያ ሕዝብ ጠላት ብዬ ያሰቀመጥኩትን ቡድን፤ በኢትዮጵያ ሕዝብ ላይ ይሄን! ወይንም ያንን! ሠራ ብዬ መግለጫ በማውጣት ውግዘት አላሽጎደጉድም። ጠላት ከዚያ የተለዬ ምን ሊያደርግ ኖሯልና! ጠላቴ ብዬ ፈርጀዋለሁ እኮ! ይልቅስ ይሄንን ጠላት ብለን የፈረጅነውን አካል፤ በተግባር በመተባበር ለመጣል በአንድነት እንሰለፍ።

The post በመቶዎች የሚቆጠሩ ጋዜጣዊ መግለጫዎች – አንዱዓለም ተፈራ – የእስከመቼ አዘጋጅ appeared first on Zehabesha Amharic.

Viewing all 15006 articles
Browse latest View live