Quantcast
Channel: Ethiopian News | ዘ-ሐበሻ | Latest News Provider | News For All
Viewing all 15006 articles
Browse latest View live

ሐጂ ነጂብ መሐመድ ይናገራሉ –ልዩ ቃለምልልስ | Audio

$
0
0

Haji

የፕ/ት ኦባማን ያለፈው ሳምንት በአሜሪካ ስልጣን ላይ ከወጡ የመጀመሪያ የሆነውን የባልቲሞር የመስጊድ ጉብኝታቸውን አስመልክቶ ህብር ሬዲዮ ከሐጂ ነጂብ መሐመድ የፈርስት ሂጅራ ፋውንዴሽን ፕሬዝዳንት ጋር ተወያይቷል። ሐጂ ነጂብ በአሜሪካ ስላለው የሙስሊሞች መብትና የሙስሊም ጥላቻ ስላለባቸው ዜጎች እንዲሁም ስለ ኢትዮጵያው የግፍ አገዛዝ ለሙስሊሙን ሰላማዊ ተቃውሞ ዛሬም ድረስ ስለሚሰጠው የሀይል ምላሽና ለዘመናት በሰላም አብሮ የኖረውን ክርስቲያንና ሙስሊም ለማዳማት ስለሚያደርገው ገደብ የለሽ ቅስቀሳ ጭምር ተጠይቀው መልሰዋል። ይከታተሉት።

The post ሐጂ ነጂብ መሐመድ ይናገራሉ – ልዩ ቃለምልልስ | Audio appeared first on Zehabesha Amharic.


የቪኦኤው ጋዜጠኛ “አርበኞች ግንቦት 7 በትክክል ምን እየሠራ እንደሆነ ሊነግሩን ይችላሉ?”ሲል ጠይቋል፤ ፕ/ር ብርሃኑ ነጋም ይመልሳሉ |ክፍል 2 እና የመጨረሻው ቃለምልልስ

$
0
0


የቪኦኤው ጋዜጠኛ “አርበኞች ግንቦት 7 በትክክል ምን እየሠራ እንደሆነ ሊነግሩን ይችላሉ?” ጠይቋል፤ ፕ/ር ብርሃኑ ነጋም ይመልሳሉ | ክፍል 2 እና የመጨረሻው ቃለምልልስ
nega

The post የቪኦኤው ጋዜጠኛ “አርበኞች ግንቦት 7 በትክክል ምን እየሠራ እንደሆነ ሊነግሩን ይችላሉ?” ሲል ጠይቋል፤ ፕ/ር ብርሃኑ ነጋም ይመልሳሉ | ክፍል 2 እና የመጨረሻው ቃለምልልስ appeared first on Zehabesha Amharic.

ማንስ ኦሮሞን በኦሮማዊነት ያማል? |ከታሪኩ አባዳማ

$
0
0

አንድ ዠብራራ ወያኔ በማህበራዊ ገፅ ላይ ሲመፃደቅ አገኘሁት – ነገሩ አባይ ፀሀዬ የሚባል ቱባ ወያኔ በል ሲለው እየተነሳ ‘…ልክ እናስገባችሁዋለን…’ እያለ መደንፋቱ ካስከተለው ቀወስ ጋር ተያይዞ የመጣ ጉዳይ ነው። አባይ በድንፋታ የዘባረቀው ፀያፍ ቃል በህዝብ ስሜት ውስጥ ያሳደረውን ቁስል እና አሉታዊ ዝንባሌ ለማስታገስ በሚል ‘እኔ ይህን አላልኩም – የኦሮሞ ህዝብ ማን እንደበደለው ያውቃል…’ ሲል ጣቱን ወደ ሆነ አቅጣጫ ለመጠቆም እየደዳው ማስተባበያ ቢጤ ይደሰኩራል። ማስተባበያ በሉት ማብራሪያ ይዘቱ ያው የተለመደው የወያኔ የዘር ልክፍት ድንፋታ ከመሆን የዘለለ ፋይዳ የለውም።

Oromo
ታዲያ ግልገል ወያኔው ጉዳዩ በደንብ እንደገባው ሊያብራራልን ከጅሎ ‘የኦሮሞ ህዝብ አዳማን ማን ናዝሬት እንዳላት ፣ ቢሾፍቱን ማን ደብረዘይት እንዳላት ያውቃል’ የሚል ጨቅላ እንቶ ፈንቶ ይለጥፋል። ይህን ከቁም ነገር ቆጥሮ ቴድሮስ አድሀኖም የተባለው የወቅቱ የወያኔ ውጪ ጉዳይ ሀላፊ ደግሞ የግልገል ወያኔውን ማብራሪያ like አድርጎ እሱም በዚህ ተራ ፕሮፓጋንዳ እንደሚስማማ ያረጋግጣል። ህዝብን ከህዝብ ማጋጨት ይጠቅማል ከተባለ ግልገሉም ቱባውም ወያኔ ባንድ ረድፍ ተሰልፎ ሲያራግብ ታገኙታላችሁ – የወያኔ ብስል የለውም። ጉዳዩ ብዙ ግምት የሚሰጠው ባይሆንም የወቅቱ ህዝባዊ አመፅ ወያኔን ከግልገል እስከ አውራዎቹ ምን ያህል እያወራጨ መሆኑን ያለጥርጥር ያሳያል።

ናዝሬት ወይንም ደብረዘይት የሚል ስያሜ ከአንድ ከተማ መቆርቆር ጋር ተሳስሮ የመጣ አካባቢው ባንድ ታሪካዊ ወቅት በይዘቱ መለወጡን የሚያመለክት ለውሱን ክልል የተመረጠ መለያ መሆኑ ግልፅ ነው። ሊታወቅ የሚገባው ጉዳይ ግን አዳማ ከናዝሬት ፣ ቢሾፍቱም ከደብረዘይት የሰፉ ብዙ ትናንሽ ከተሞችን ጨምሮ የገበሬ መንደሮችን ያቀፉ ወረዳዎች መሆናቸው ናቸው – ከቶውንም የአዳማ ወይንም የቢሾፍቱ ስም ተቀይሮ የሚያውቅ ጉዳይ አልነበረም። በአዳማ ወረዳ ናዝሬት ፣ ሶደሬ ፤ በቢሾፍቱ ወረዳ ደግሞ ደብረዘይት እና ሞጆ እንዲሁም ዱከም ሌሎችም ትናንሽ ከተሞች መኖራቸውን ሁሉም ያውቃል። አዲሶቹ ሹማምንት እነሱ እንግዳ ስለሆኑበት አካባቢ የጠለቀ ዕውቅት ስለሚጎድላቸው ሁሉም ነገር የተጀመረው እነሱ ስልጣን ከተቆናጠጡ ወዲህ ይመስላቸዋል።

አሁን ጥያቄው አዳማን እና ቢሾፍቱን በልማት ስም ወረራ በመፈፀም የመሬቱን ባለቤት አራሽ ገበሬ ካላንዳች የህይወት ዋስትና እያፈናቀለ ያለው ስግብግብ ቀማኛ ማነው የሚለው ነው!

እንጂ ጉዳዩ ስለ ከተማ ስም ከሆነ መርካቶ ፣ ፒያሳ ፣ ፖፖላሬ ፣ ካዛንቺስ አማርኛ አይደሉም። ጣሊያን ሲቆረቁራቸው ያወጣላቸው ስም ነው – ይህም አካባቢው ባንድ ታሪካዊ አጋጣሚ መለወጡን ጭምር የሚያመለክት ነው። መርካቶ በሉት ፒያሳ ይኸው እስከ ዛሬ ህብረተሰቡ ይጠቀምባቸው የለም? ቴድሮስ አድሀኖም ያደጉትስ አስመራ ኮምፐሸታቶ አልነበረም እንዴ ወይንስ ገዛ ባንዳ ይሆን?
የጣሊያንኛ ነገር ከተነሳ ሸሚዝ ፣ ካልሲ ፣ አንሶላ ፣ ሙታንታ ስንል የምንጠቀምባቸው ብዙዎቹ ዘመን አመጣሽ ቁሳቁስ አሁንም ቢሆን በራሳችን ቋንቋ ስም የላቸውም – ምን ችግር አለው?

እነ ኮልፌ ፣ ጉለሌ ፣ ኮተቤ ፣ ገፈርሳ የቀድሞ ስያሜቸውን ሳይሽሩ መቆየታቸውስ ምን ያመለክታል። እነ ቴድሮስ አዳኖም የኦሮሞ ስያሜ ያላቸው ስፍራዎች ላይ ዘመቻ ተከፍቶ በሙሉ በአማርኛ እንደተተኩ እና ይህም እንደ ጠላትነት እንዲቆጠር የፖለቲካ ነጥብ ማስቆጠር ይሻሉ። ይሁንና ጉዳዩን ስንመረምር እነኝህ ወያኔዎች ምንም ትንሽ ቢሆን አንድን ህዝብ ከለሌላ ጋር ለማጋጨት ይጠቅማል ብለው ካሰቡ ስለሚያወሩት ነገር ላፍታ ጉዳዩን ለማጤን እንኳ አይፈልጉም – በቃ ተነስቶ አፍ መክፈት ብቻ ነው ፤ እኛም በተከፈተ አፋቸው ጭንቅላታቸውን ለማየት እና ለመታዘብ እንገደዳለን።
ስለ ስም አወጣጥ ማህበራዊ እውነታ ትንሽ እንዲማሩም በዚህ አጋጣሚ ሀሳብ እናካፋልቸዋለን።

ሰፋ ያለ አግዳሚ መቀመጫ ያለውን ታክሲን ውይይት ብሎ ህብረተሰቡ ስም ሲሰጠው በጊዜው አንድ የተለወጠ ነገር መኖሩን ያመለክታል። ጠ/ሚኒስትር ደሳለኝ ሀ/ማርያም ሶስት ረዳት ምክትል ጠ/ሚኒስትሮች ሲመደቡባቸው በህብረተሰቡ ዘንድ ባጃጅ ጠ/ሚኒስትር የሚል ስም እንደወጣላቸው ሰምቻለሁ። ባጃጅ የሚሏት ታክሲ ባለ ሶስት እግር ጎማ መሆኗን በማጣቀስ… በሶስት ጎማ ኩር ኩር የምትል ታክሲ።
መለስ ዜናዊ ባንድ ወቅት አንድ የአሜሪካ የፓለቲካ ሰው ‘ትግላችሁ ብሔረሰብ ነፃነት ዙርያ ያጠነጠነ መሆኑ አገሪቱን አይጎዳም ወይ’ ብሎ ሲጠይቀው ‘ትግላችን የአማራን በተለይም የሸዋ አማራን ትምክህተኝነት ለማስወገድ ነው’ ብሎ መልስ መስጠቱን ብዙዎቻችሁ ታስታውሳላችሁ። ሸዋ ላይ ያነጣጠረው የወያኔ ትግል ሸዋ የሚባል ለምእተ ዓመታት የቆየ ብዙ ብሔር ብሔረሰቦችን ያቀፈ ክፍለ ሀገር ከኢትዮጵያ ካርታ ላይ ጨርሶ አንዲሰረዝ በማድረግ ተጠናቋል። ዛሬ የሸዋ ሰው የሚባል የለም – ሸዋ ደግሞ የማንም ብሔረሰብ ንብረት አልነበረም – ከሁሉም የአገሪቱ ማእዘናት የመጡ ዜጎችን ጨምሮ ጉራጌው ፣ ኦሮምው ፣ አማራው ፣ ከምባታው ፣ ሀድያው … ወዘተ የተሰበሰቡበት ፣ በጋራ ተከባብረው በኢትዮጵያዊነት ስሜት የሚኖሩበት ክልል ነበር። ሸዋ ኢትዮጵያዊነት የተወሀደበት እንጂ የማንም አልነበረም።

በሸዌነት የሚከሰሰው ደርግ በዘመኑ ጥናት ላይ ተመስርቶ እንዲስተካከሉ ካደረጋቸው የክልል ስያሜዎች መካከል – ትግሬ ወደ ትግራይ ፣ ወላሞ ወደ ወላይታ እንዲሁም በጌምድር ወደ ጎንደር መቀየራቸው ይገኙበታል። ፊውዳሊዝም ዘመኑን ጠብቆ የተፈጥሮ ሞት ሲገጥመው መሻር የሚገባቸው ነገሮች እንዲህ ተሽረዋል። ይህ የተደረገው ግን በስሜታዊነት ወይንም አምባጓሮ ለመቀስቀስ አልነበረም። ተገቢው ጉዳይ ተገቢ ስፍራ እንዲይዝ ለማድረግ ሲባል ብቻ የተደረገ ይመስለኛል። የተዛባ ነገር ካለ ቀኑን ጠብቆ ማስተካከል ይቻላል – ለተራ የፖለቲካ ሸፍጥ መቀስቀሻ መጠቀም ግን ደካማነት ብቻ ሳይሆን የጥፋት መልዕክተኛነት ነው።

በዚያው የደርግ አስራሰባት ዓመታት በአስራምስት ኢትዮጵያዊ ቋንቋዎች ፊደል ማስቆጠር ተጀምሮ እንደነበር አስታውሳለሁ። ይህ ጥረት ሲጀመር ከሌሎች ጋዜጠኞች ጋር ሆኜ ትምህርት ሚኒሰቴር ያደረገውን ዝግጅት ለመጎብኘት ዕድል አግኝቼ ነበር። በቂ ምርምር እና ጥናት ተደርጎበት ፣ ዘላቂነት ባለው መልኩ በሚዳብርበት መንገድ ተይዞ ነበር ማለት ግን ባይቻልም ሙከራው ነበር – በጎ አጀማመር መሆኑንም መካድ አይቻልም። አፈፃፀሙን ለማሳካት አቅም ነበር ወይ የሚለው ጥያቄ ግን የተጤነ አልነበረም።
የተነሳሁበት ጉዳይ ተለጠጠ… የኢትዮጵያ ነገር ሆነና ተዛማኝ ጉዳዮችን መጠቃቀስ ገባሁ…
አዎ የኦሮሞ ህዝብ ጠንቅቆ ያውቃል…

ኦሮሞ ለኢትዮጵያ ነፃነት ፣ ክብር እና ዳር ድንበር መከበር በባለቤትነት የታገለ ፣ የሞተ እና ድል የተጎናፀፈ ክቡር ዜጋ ነው። ኢትዮጵያ ክፉ ቀን በገጠማት ታሪኳ ሁሉ በተለይም ከዘመናዊ አስተዳደር ምስረታ ጥረት እስከ አለም አቀፍ ዕውቅና ትግል ሂደት ውስጥ የኦሮሞ ደም እና ላብ ፣ ዕውቀትና ጉልበት ወይንም የተፈጥሮ ሀብት አና ጥሪት በጉልህ ደረጃ ያልፈሰሰበት አንዳችም የታሪክ ምዕራፍ የለም።
የማወራው ስለ አያና ብሩ ፣ አበበ ቢቂላ ፣ አብዲሳ አጋ ወይንም ሀይሌ ፊዳ ብቻ አይደለም – ከዚያ የጠለቀ የሰፋ ጉዳይ ነው። ህልውናችን በጀግኖች አባቶቻችን አጥንት እና ደም ተጠብቆ ቆየ ስንል እነኛ አባቶች ያለፉበትን ውጣ ውረድ በምን መለኪያ እንገልፅዋለን ፣ በምን መስፈርት እናበራራዋለን? እንደሚመስለኝ ኢትዮጵያን ጠብቆ ያቆየን ማን እንደሆነ ተጨንቀን ማሰብ እንዳንፈልግ ተደርገናል። እንዲህ እንደ አሁኑ ዘመን ፈተና ላይ ስንወድቅ ግን ዞር ብለን የነበረውን እንደ ሰበር ዜና ለማወቅ እንገደዳለን።

ለኢትዮጵያ ህልውና ሲሉ የኦሮሞ ልጆች በመጀመሪያው ረድፍ ላይ ተሰልፈው ደማቸውን ገብረዋል። እነ ገረሱ ዱኪ ፣ በቀለ ወያ ፣ ደላሳ ጎቡ ፣ ጃ ጋማ ኬሎ ፣ አብዲሳ አጋ… የቅርቦቹ እነ ደምሴ ቡልቶ ፣ መርዳሳ ሌሊሳ ፣ ባጫ ደበሌ… ሚሊየኖች ዘርዝሮ ማቅረብ ይቻላል… ኦሮሞ ለኢትዮጵያ ክብር ሲል እንዲህ መራራ መስዋዕትነት ሲከፍል መቆየቱ ደብዘዝ ያለባቸው ከኦሮሞውም ከኦርማውም በረከትከት ያሉ ይመስላል – የስማዕቱ የሀይማኖት መሪ አቡነ ጴጥሮስ ኦሮሞነት ሰበር ዜና የሆነባቸው አይነት ማለቴ ነው።

ታላቁ የኢትዮጵያ ስማዕት አቡነ ጴጥሮስ ውልደት ስማቸው መገርሳ በዳዳ መሆኑ አዲስ ታሪክ የሆነባቸው እንዳሉ ሳትታዘቡ አይቀርም። የሀይማኖት መሪዎች ለከፍተኛው የሀይማኖት መሪነት ሲጠሩ ስማቸውን ከመፅሀፍ ቅዱስ ከሚገኙ ቅዱሳን ስሞች አንዱን ይወርሳሉ። ነገስታትም ፣ ‘ታጋዮችም’ እንዲሁ – አፄ ሀይለስላሴ ተፈሪ መኮንን ፣ በዝብዝ ካሳ አፄ ዮሀንስ እንደ ነበሩ ሁሉ። መለስ ዜናዊ ለገሰ ፣ አባዱላም ምናሴ እንደ ነበሩ ሁሉ። ይህ በኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን በመላው አለም ሲሰራበት የቆየ ወግ ነው።

ባለፈው ሰሞን “እኛም ኦሮሞዎች ነን” በሚል ርዕስ ከትግራይ ክልል የተገኙ ግማሽ ደርዘን የሚሆኑ ወገኖች ተጠራርተው ያንፀባረቁትን ትብብር ሳነብ ያሳደረብኝን ስሜት እዚህ መግለፅ ፈልጋለሁ። ምኞታችን ፍትሀዊ ስርዓት እንዲሰፍን መሆኑ እሙን ነው። ትናንት እንደ ሰለጠነው አለም ሁሉ ጭቆናን ፣ አፈናን እና ብዝበዛን በዚህ በዚያ መደቦች የጋራ ትግል እናስወግዳለን ስንል እንዳልነበር ሁሉ ለወያኔ ምስጋና ይግባውና ትግሉ በብሔር ብሔረሰብ ተወላጆች መካከል የሚደረግ ትብብር ጉዳይ እንዲሆን ጊዜው ግድ ብሏል።

ወዛደሩ ለአርሶ አደሩ ትግል የጀርባ አጥንት ነው በሚለው ምትክ ፤ ተራማጅ ምሁር ከጭቁን ህዝቦች ጎን ይሰለፋል በሚለው ምትክ ዛሬ ጨዋታው ትግሬ ከኦሮሞ ፤ ኦሮሞ ከአማራ… ከዚህ ከዚያ ብሔረሰብ ድጋፍ እና ግንባር መፍጠር የሚል ሆኗል። ለፍትሀዊ አንድነት ሳይሆን ለጎጣዊ ምንነት መስፈን እንድንታገል በወያኔ መገደዳችን ገሀድ ይታያል። እናም የዚህ ብሔር ብሔረሰብ አባላት የትግል አጋርነት ለዚያኛው ብሔር ብሄረሰቦች ትግል ተገለፀ ወደሚል ደረጃ ዝቅ ብለናል – ዕድሜ ለወያኔ።

ግን በዚህ የትግል ሂደት የሚረጋገጠው የፍትህ እና የህግ በላይነት ወይንስ የብሔር ብሔረሰብ ነፃነት? እና ውጤቱ ኢትዮጵያ የተነፈገችውን ፍትሀዊ ስርዓት ማስፈን ወይንስ ካንዱ የጎጥ መንግስት ወደ ሌላ ሽግግር? ወይንስ አስከናካቴው ኢትዮጵያ ባለቤት የሌላት ፣ ተቆርቋሪ የሌላት እንደ አየር ተንና በመክሰም ላይ ያለች አገር? ሁኔታው አሳሳቢ ነው።

እነ ዶክተር መሳይ ከበደ እንኳ ሳይቀሩ ዛሬ ጭንቀታቸው እንዴት ኦሮሞ ሲነሳ ሌላው ብሔረሰብ ዝም ብሎ ይቀመጣል? የሚለው ጉዳይ ሆኗል። አልፈርድባቸውም – ምን ምርጫ አለ። ይሁንና አራት አመታት ሙሉ የፍልስፍናን ጥበብ ያስተማረኝ ምሁር ፣ ፍትህ አንፃራዊ ቢሆንም መደባዊም ነው ብሎ ያስጠናኝ የጥበብ ሰው ዛሬ የብሔረሰቦች ትብብር ጥሪ ውስጥ ተዘፍቆ ሳየው አዝናለሁ። ይህ ጉዞ ወቅታዊነቱ ስህተት ነው ማለቴ ሳይሆን በሁሉም አቅጣጫ ወያኔ በፈጠረው ኩሬ ውስጥ ተደፍቀን መገኘታችን ግን ጉዳዩ ለዘለቄታው ምን ያህል አሳሳቢ መሆኑን ለማመልከት ነው።

ህብረተሰብን በመደብ ከፋፍሎ በዚያ መሰረት ሊሰፍን ስለሚገባው ፍትሀዊ የሀብት ስርጭት ፣ የፖለቲካ ተሳትፎ ድርሻና ስለሚጠይቀው የሰብአዊ መብት መስፈን ጉዳይ መነጋገር ጊዜው ያለፈበት የፋራ አጀንዳ ሆኗል። ባለ አገር ሳይሆን ዛሬ የሚያኮራው ባለ ብሔረሰብ መሆን ነው – የወርቅ ብሔረሰብ… የታጋይ ብሄረሰብ ፣ የሀብታም ብሄረሰብ ፣ የጭቁን ብሔረሰብ… ስልጣን ለመጋራት ጥሮ ግሮ የብሔረሰብ ነፃነት ማወጅ… የብሔረሰብ ነፃነት ገበያ ደርቷል።

የመደብ ትግል ጥያቄ ሳይነጋ የመሸበት ፣ ሳይዳክር ወገቡ የጎበጠበት ታሪካዊ ውነት ሆኗል። የመደብ ትግሉ ሰራዊት በአይነቱም በይዘቱም ውጥንቅጡ የወጣ የጋራ በሚለው የመደብ ጠላት ላይ እንኳ ባንድ ረድፍ ተሰልፎ የመፋለም ብቃት የጎደለው ሰነፍ ሆኖ ተገኝቷል። እናም ድሉ አዲስ ውነት አለን ብለው በተሰለፉ የብሔረሰብ ነፃ አውጪዎች እጅ ወድቋል – የብሔር ብሔረሰቦች ነፃነት እስከ መገንጠል…
እኔ አስከሚገባኝ ድረስ ኢትዮጵያ የብዙ ቋንቋዎች እና ባህሎች ባለፀጋ ናት። ስለ ኢትዮጵያ ስንናገር ስለ ነኝህ የተለያየ ቋንቋ እና ባህል ባለቤት ህዝቦች ነው። እናም የትኛውም ኢትዮጵያዊ ቋንቋ አድጎ በልፅጎ የመማሪያ ፣ የመመራመሪያ ቋንቋ መሆን ቢበቃ ኩራቱ የኢትዮጵያ ነው። ባህሉ ተጠብቆ ዳብሮ ቢቀጥል አሁንም ኩራቱ የኢትዮጵያ ነው። ይሄ ሁሉንም ኢትዮጵያዊ ቋንቋ የሚመለከት ነው።
ጉዳዩ የሁሉም ኢትዮጵያዊ እንጂ ያንድ ወይንም የሌላ ብሔረሰብ ሰዎች የግል ጉዳይ ተደርጎ መታየት የለበትም። ይሔ ወይም ያ ብሔረሰብ የግሌ የሚለው ኢትዮጵያን የማያኮራ ፣ የማያደምቅ አጀንዳ ይዞ ቢነሳ አካሄዱ ንትርክ እና አማባጓሮ ከማስነሳቱ በስተቀር ለህዝቡ የሚፈይደው ነገር አይኖርም።

ህብረተሰብ ዳይናሚክ ነው – ይዳብራል ፣ ያድጋል ፣ ይለወጣል – የሚለወጠው እና የሚዳብረው ከቋንቋው ፣ ከባህሉ ፣ ካኗኗሩ ፣ ከመስተጋብሩ… ከብዙ ክስተቶች ጋር ነው። ህብረተሰባችን እየተለወጠ ሲሄድ ብሔራዊ ምንነቱን ይበልጥ ማሸብረቅ በሚችልባቸው ቋንቋዎቹ የጥበብ እና ምርምር ውጤቶች ተጠቃሚ እየሆነ እንጂ ባለበት እየረገጠ አይደለም። የብዙ ቋንቋዎች ባለቤት መሆናችን ለውሱን አመለካከት እና ጠባብ አላማ ሰለባ ሊያደረገን አይገባም። ጉዳዩ የሰብአዊ ርህራሄ እና የበጎ ፈቃድ ሳይሆን ዕድገት እና ዘመን ግድ የሚለው እርምጃ ነው። ትናንት መደበኛ መሰረታዊ ትምህርት ይሰጥ የነበረው በአማርኛ ቋንቋ ብቻ ነበር። ነገ አቅሙ ከፈቀደልን በሌሎች ኢትዮጵያዊ ቋንቋዎች ትምህርት የማይሰጥበት ምን ምክንያት አለ? አንድን ቋንቋ አዳብሮ እና አበልፅጎ የምርምር ማካሄጃ ደረጃ ላይ ማድረስ የዕድገት ውጤት ነው።

አፄው እና የጉልተኛ ስርዓቱ የተገረሰሰው በብሔር ብሔረሰቦች ግምባር ሳይሆን ግፍና ብዝበዛ ይወገድ ብለው በተነሱ ስለ ፍትህ እና የአገር አንድነት የጋራ ራእይ በነበራቸው ከሁሉም የኢትዮጵያ ማእዘናት በተነሱ እንግልት ዜጎችና አጋር ሆነው በተሰለፉ ተራማጅ ምሁራን ትግል መሆኑን መዘንጋት የለብንም። ለዘለቄታው ፍትሀዊ ስርዓት ማምጣት ባይበቃም ምልአተ ህዝቡ ግን ታሪካዊ ድል መጎናፀፉ ውነት ነው።
የጣሊያን ወረራ በሉት የሶማሊያ መስፋፋት የተገታው እና የተደመሰሰው በሁሉም ዜጎች ሙሉ የባለቤትነት ተሳትፎ በተካሄደ ርብርብ ነበር። የብሔረሰብ ነፃ አውጪዎች ትግል በዚህ ሂደት ውስጥ ያበረከተው አንዳችም በጎ ነገር የለም። እንዲያውም ኢትዮጵያውያን በጋራ ተሰልፈው የዚያድ ባሬን ወረራ ለመመከት ሲዋደቁ የትግራይን ብሔረሰብ ነፃ እናወጣለን ያሉ የወያኔ መሪዎች በሱማሊያ ፓስፖርት እና ጦር መሳሪያ ድጋፍ በኢትዮጵያ ህልውና ላይ ሴራ ይደቁሱ ነበር – ለወያኔዎቹ ኢትዮጵያ ወረራ ቢፈፀምባት ፣ ያን ጊዜ ዚያድ ባሬ በለስ ቀንቶት ቢሆንና ኢትዮጵያ ብትፈራርስ ደንታቸው አልነበረም።

ለብዙሀኑ ዜጋ ግን በወረራው የተደፈረችው አገር ነበረች ፣ የታደጓትም ዜጎቿ ነበሩ። ያኔ ከፋም ለማም አገር ብለው የሚያስተዳድሩ መሪዎች ነበሩን… እነሱ ባቆዩት አገር ውስጥ ነው እንግዲህ ዛሬ ለብሔረሰብ ነፃነት እስከ መገንጠል ለመታገል የሚጠራሩት።
በወዛደሩ ፣ በአርሶ አደሩ ፣ በጭቁኑ መለዮ ለባሽ እና ተራማጅ ምሁራን የጋራ ግንባር ኢትዮጵያ ትለመልማለች የሚለው ስሜት ቢያንስ ቢያንስ ደብዝዟል – ያንን መርሆ ኮለኔሉ ለስልጣናቸው መደላደያ አድርገው ስላረከሱት ፋይዳው ወድቋል።
አዎ የኦሮሞ ህዝብ ጠንቅቆ ያውቃል…

ጀግኖቹ የኦሮሞ ልጆች እንደ ማንኛውም ኩሩ ኢትዮጵያዊ ሁሉ ጣልያንን ሲዋጉ ፣ የሱማልያን ወረራ ለመመከት ሲዋደቁ ፣ ተገንጣዮችን እና አስገንጣዮችን ሲፋለሙ ፣ አገሬን አሳልፌ ለማንም ስግብግብ ወራሪ አሳልፌ አልሰጥም ሲሉ… አቡነ ጴጥሮስ የፋሺስት ግፋዊ ፍርድ አስፈፃሚ በሆኑ ባንዳ ተኳሾች በጥይት ሲደበደቡ ጉዳዩ አገርን እንደ አገር ለማቆየት ሲባል የተፈፀመ መሆኑን ማንም ሊዘነጋው አይገባም።
የዛሬው ትውልድ ወያኔ ከዘረጋው የጥፋት ወጥመድ ውስጥ ወድቆ የማይሽር ጉዳት ከመድረሱ በፊት ስልት እና ግብ ላይ ያነጣጠረ ተግባር መከናወን ይገባዋል። ብሔረሰቦቻችን መኩሪያችን ናቸው – ብሔረሰቦቻችን የታቀፉባት ኢትዮጵያ ከሌለች ሁሉም ነገር ይቀራል። ኢትዮጵያን አጥፍቼ እኔ በነፃነት እኖራለሁ የሚል ብሔረሰብ ካለ አካሄዱ ግብዝነት ብቻ ሳይሆን አርቆ ማስተዋል የጎደለው ዝንባሌ ነው። የቆጡን አውርድ ብላ የብብቷን ጣለች እንዳይሆን ጉዳዩን ማስተማር የሁሉም ሀላፊነት የሚሰማቸው ዜጎች ድርሻ ነው።
ሉአላዊነት የሌለው ህዝብ አንድም አገሩን የተቀማ ፣ ብሔራዊ ክብሩን የተገፈፈ ፣ ወሰኑ እና ዳር ድንበሩ እንዳሻ የሚጠብ እና የሚሰፋ ብሎም እንደ ዜጋ ምንም አይነት የባለቤትነት ድርሻ የሌለው ማለት ነው።

አገር ፣ ብሔራዊ ማንነት ለይስሙላ ወይንም ለፈሊጥ የሚኖር ሳይሆን ከግለሰብ እስከ ህብረተሰብ ብሎም ብሔር እና ብሔረሰብ ህልውናቸው ተረጋግጦ ፣ ዋስትና አግኝቶ በስርአት የሚተዳደሩበት ማዕቀፍ ነው። አገር የተለያየ ቀለም ፣ ቋንቋ ፣ ባህል ስነ-ልቡናዊ ዝንባሌ ባላቸው ህዝቦች ታሪካዊ ትስስር ተፀንሶ በተለያየ ዕድገት ጎዳና ፣ ውጣ ውረድ ፣ መውደቅ እና መነሳት ያልፋል – ይሄ በሁሉም የአለም አገሮች ታሪክ ውስጥ የሚገኝ ውነት ነው። አገሮች ያንን የዕድገት ደረጃ አልፈው ዛሬ እንደ ፍትህ ፣ ሰብአዊ መብት ጥበቃ እና የህግ በላይነት ጉዳዮች ያሉ ይበልጥ የሚዳብሩበትን ብልሀት የሚመረምሩበት ዘመን ላይ ናቸው።

ሀይሌ ገ/ሥላሴ የተባለው እውቅ አትሌት ሰሞኑን ቢቢሲ ራዲዮ ላይ ቀርቦ ሲናገር ‘…ለአፍሪካውያን ዲሞክረሲ የቅንጦት ጥያቄ ነው’ ማለቱን ሳታዳምጡ አልቀራችሁም። አቃቂ እና ዱከም አካባቢ በሺዎች የሚቆጠሩ ገበሬወች ከአፅመ ርስታቸው ተፈናቅለው በሪል ስቴት ስም ሀይሌ ገ/ሥላሴ ኮንዶ እየገነባባቸው መሆኑን ከፊሉንም የተንጣለለ የግጦሽ መሬት በራሱ ስም አጥሮ ማስቀመጡን ሳታውቁ አትቀሩም። ከአካባቢው የተነፈናቀሉ ዘመዶች ስላሉኝ ጉዳዩን በቅርብ አውቃለሁ። ዛሬ ህዝቡ ተነስቶ የመሬት ወረራ ይገታ ብሎ መሰረታዊ የሰብአዊ መብት ጥያቄ ማንሳቱ ለገ/ሥላሴ ልጅ የቅንጦት ጥያቄ ሆኗል። የድህነትን ዳገት በሩጫ የወጣው አትሌት ስለ ዲሞክረሲ ፅንሰ ሀሳብ ለማወቅ ዕድል የነበረው አይመስለኝም። እሱ ዛሬ የቅንጦት ህይወት ውስጥ እንዳለ ሳልዘነጋ ስለ ዲሞክረሲ ማይም ቢሆንም ስለ ቅንጦት ጉዳይ ግን የጠለቀ ዕውቀት እንዳካበተ አልጠራጠርም። የስንቱን አንጎል አንይ!

ለተፈናቀሉት ዘመዶቼ የገ/ሥላሴ ልጅ ሌላ ስግብግብ ወራሪ እንጂ ጀግና አይደለም።
ተነሱ እናንት የርሀብ እስረኞች
ተነሱ የምድር ጎስቋሎች
ፍትህ በሚገባ ይበየናል
ሻል ያለ አለምም ይታያል…
አዎ የኦሮሞ ህዝብ ጠንቅቆ ያውቃል…
የኦሮሞ ህዝብ ጥያቄ የሁሉም ኢትዮጵያዊ ጥያቄ ነው – የመሰረታዊ ሰብአዊ መብት ጥያቄ ነው ፤ የአገር ሉአላዊነት ጥያቄ ነው። ስለሆነም ዘረኞችን እና ስግብግብ ዘራፊዎች ወደ ታሪክ አተላነት እስከሚቀየሩ ድረስ ትግሉን ይቀጥላል።
ኦሮሞን ኦርመ ሚቲ – ኢትዮጵያ ኦርማፍ ሂንላቱ!!

The post ማንስ ኦሮሞን በኦሮማዊነት ያማል? | ከታሪኩ አባዳማ appeared first on Zehabesha Amharic.

የጊብሰን ዩዝ አካዳሚ ጉዳይ |መልካም አስተዳደርን ጥያቄ ምልክት ውስጥ የከተተው ደብዳቤ

$
0
0

ጊብሰን ዩዝ አካዳሚ የሚባለው ትምህርት ቤት የከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናትንና የጄኔራሎችን ልጆች በስኮላርሺፕ ስም በነፃ የሚያስተምር መሆኑ የአደባባይ ሚስጥር ነው፡፡ ይህ ት/ቤት በአገሪቱ ውስጥ ከፍተኛ ክፍያ የሚያስከፍል ሲሆን በአመት ወደ400 ሚሊዮን ብር ከወላጆች ያገኛል፡፡ ይህ አልበቃ ብሎት በየአመቱ ከፍተኛ ጭማሪ እያደረገና በተለያዩ መንገዶች ህገ ወጥ ስራዎች ላይ እየተሰማራ በመገኘቱ የማስተማር ፍቃዱ ተሰርዟል፡፡ የት/ቤቱን የማስተማር ፈቃድ መሰረዝ የሚገልፀውን ደብዳቤ እነሆ አቅርበናል፡፡

ይሁን እንጂ ይህ ደብዳቤ በአገሪቱ ውስጥ የተንሰራፋው የመልካም አስተዳደር ችግርን ጥያቄ ምልከት ውስጥ የሚከት ነው፡፡ አንዱ የሰረዘውን ደብዳቤ የሚሰርዝ ሌላ አካል ካለ የምናየው ይሆናል፡፡ መንግስት ራሱ ያወጣውን ህግ ራሱ የማስፈጸም ችግር እንዳለበት የዚህ ትምሀርት ቤት ጉዳይ ትልቅ ማሳያ ይሆናል፡፡ ምክንያቱም የከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናትና የጄኔራሎች ልጆች በነፃ እያስተማረ ይህ ደብዳቤ ተግባራዊ ይሆናል ማለት ዘበት ነው፡፡ በዚያ ላይ ይህ የ400 ሚሊዮን ብር ቢዝነስ ጉዳይ ስለሆነ ለሙስና ቅርብ ነው፡፡ ስለዚህ በዚህ ደብዳቤ በስፋት በተገለፀው ህገወጥ ተግባር የተነሳ ጊብሰን ዩዝ አካዳሚ በሚቀጥለው አመት ማስተማር ቢከለከልም ማስተማሩን እንደሚቀጥል ከወዲሁ መገመት እንችላለን፡፡

ይህ ኢትዮጵያ ነዋ!!!!!
gibsen 1

gibson 2

gibson 3

gibson 4

The post የጊብሰን ዩዝ አካዳሚ ጉዳይ | መልካም አስተዳደርን ጥያቄ ምልክት ውስጥ የከተተው ደብዳቤ appeared first on Zehabesha Amharic.

እውን ጥላሁን ገሠሠን በስለት ለመወጋት ያበቃው የ’ሆድ ይፍጀው’ምስጢር ይህ ይሆን?

$
0
0

ልዑል ዓለሜ የተባሉ የዘ-ሐበሻ ተከታታይ ጥላሁን ገሰሰ እስከ እለተ ሞቱ ድረስ አፍኖት የሞተው ምስጢር ‘ሆድ ይፍጀው” ጉዳይ ይህ ነው  በሚል አንድ ጽሁፍ አድርሰውናል:: ጥላሁን በሕይወት ስለሌለ አሁንም ይህንን ጉዳይ ከርሱ አንደበት ማረጋገጥ ባይቻልም የጸሀፊውን ምስጢራዊ ጽሁፍ ለግንዛቤ አስተናግደናል::

tilahun

የጥላሁን ገሰሰ ( ሆድ ይፍጀዉ ) ሚስጥር
የወጋ ቢረሳ የተወጋ አይረሳ ! !
ጥላሁን ገሰስ መስከረም 27 1940 ዓ/ም ከእናቱ ከወ/ሮ ጌጤ ጉርሙ ከአባቱ ከአቶ ገሰሰ ወ/ኪዳን ተወልዶ በሚያዚያ 9/2009 ዓ/ም ከዚህ አለም በክብር ተሰናብቷል የመጀመሪያ የሙዚቃ ስራዉን በሐገር ፍቅር ቲያትር የቀረበዉ፡ የኢትዮጵያ የሙዚቃ ንጉስ ክቡሩ ሰዉ አርቲስት ጥላሁን ገሰሰ በ1960ዎቹ አመተ ምህረት አካባቢ ነበር እጅግ ታዋቃና ወርቃማናቱን በወርቃማዉ እድሜዉ ዘመን ላይ ጊዜ የማይሽረዉን አሻራ ያስቀመጠዉና ያሳየዉ ጥላሁን በዚያን በ60ዎቹ ዘመን ላይ በቅጽል ስም ዘ ቮይስ “The Voice” ተብሎ ይጠራ ነበር።
በ1970 እና 80 አካባቢዎች ላይ በሐገር አቀፍ ደረጃ ወሳኝ እና ቀስቃሽ ሙዚቃዎችን ለወገኖቹ አብርክቷል አርቲስት ጥላሁን ገሰሰ በዚሁ ሐገር ወዳድነቱና ፍቅሩ የተንሳ በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የዶክተሬት ማእረግ ከማግኘቱም ባሻገር የስነ ጥበብ ማእከላ ( Ethiopian Fine Art and Mass Media Prize Trust. ) የክብር ሽልማት ባለቤት ነዉ። 


ጥላሁን ገሰሰ ስላዘፈነዉ ነገር የለም ከቀጠሮ ጀምሮ እስከ እስከ ስራ ክቡርነት የተዳሰሰዉ በጥላሁን ገሰሰ ዜማና ድምጽ ነበር፡ ጥልዬ በደርግ ዘመነ መንግስት በሐገሪቱ ዙሪያ በተቀሰቀሰ ጦርነት ምክንያት እጅግ ቀስቃሽ ወታደራዊ ሙዚቃዎችን ግንባር ድረስ ሄዶ በማቅረብ የሚታወቅ ታላቅ የአርት አባት ነበር። 


ሚያዚያ 18/1993 የኢትዮጵያዊያን ፋሲካ እለት እሁድ ማምሻዉን በአስገራሚ ሁኔታ አርቲስት ጥላሁን ገሰሰ በመኖሪያ ቤቱ ዉስጥ በስለት ተወጋና ተገኘ። 


የዚያን እለት ከቀኑ 4 ሰአት ላይ እስጢፋኖስ ቤ/ክርስቲያን ፊት ለፊት አይሴማ ሕንጻ ስር በምትገኘ ሰለሞን ካፌ ዉስጥ አሉ የሚባሉ አንጋፋዎች ተሰባስበዋል ሰለሞን የካፌዋ ባለቤት ሚስቱ በኮሞሮስ ደሴት ላይ ከተከሰከሰዉ የኢትዮጵያ አየር መንገድ አደጋ የዳነች በወቅቱ ብቸኛ ሐብታምና የሙሶ መኪና አስመጪ፣ ሐየሎም አርአያ፣ መሐመድ አል_አሙዲን፣ እንዲሁም እዚያዉ አይሴማ ህንጻ ላይ ይኖር የነበረዉ ታደለ ይድነቃቸዉ፣ ጥላሁን ገሰሰ፣ እና የጃክሮስ ባለቤት በአንድነት ሆነዉ ሻይ እየጠጡ ተቀምጠዉ ነበር። መሐመድ አል_ አሙዲን በወቅቱ እዚያ ያዘወትር የነበረበት ምክንያት ሜላት የተባለች እጮኛዉ ( ሜላት ኮምፒዉተር ) እዚያ ሕንጻ ላይ 5ተኛ ፎቅ ተከራይታ ትኖር ስለነበር ሲሆንና የሻራተን ሆቴል በቁፋሮ ላይ ስለበር በቅርበት ለመቆጣጠርም ጭምር ነዉ።


የሻይ ቡና ፕሮግራሙ ሞቅ ደመቅ እያለ በነበረበት ወቅት አንድ የስልክ ጥሪ ከወደ ካፌዉ ወደ ጥላሁን አቃጨለች ጥላሁን የስልኩን ጥሪ ካስተናገደ ወዲህ ፊቱ ልዉጥውጥ ብሎ የነበረበት ቦታ ተቀመጠ ጉዳዩን በአንክሮ የተከታተለዉ ሀየሎም ጥላሁንን ለብቻዉ ገለል አድርጎት ምን እንደተፈጠረ ይጠይቀዋል ጥላሁንም ሌሎቹ በጥቂቱ እንደሚሰሙት እያወቀ፣…
” አነተ ዉሻ የዉሻ ልጅ!!! ተነስ ታጠቅ ዝመት እያልክ የትግራይን ህዝብ ደም ስታፈስ ኖረህ አሁን ምንም እንዳልተፈጠረና እንዳልሰራህ እዚህ ሐገር ላይ በሰላም ትኖራለህ ? በፍጹም አትኖርም “….. ሲል አንድ ግለሰብ አስፈራራኝ በማለት ይናገራል!
ሐየሎም ጥላሁን አተኩሮ ከተመለከተዉ በኋላ ደንገጥ እንደማለት ብሎ ዝምታን በመምረጡ ጥላሁን ቀደም ብሎ ሁሉንም ተሰናብቷቸዉ ሄደ! ሐየሎምም እሳት ጎርሶ እሳት ልሶ ” እነዚህ የዉሻ ልጆች አርፈዉ አይቀመጡም ” በማለት ተሳድቦ ከጥላሁን ገሰሰ እግር ተከትሎ ሄደ። 


እንግዲያዉ ማታ ጥላሁን ገሰሰ በብሔራዊ ቲያትር ዉስጥ እይዋት ስትናፍቀኝን በማንቆርቆር ህዝብን ሲያስደስት በነበረበት ወቅት ላይ የተደገሰዉ የግድያ ሴራ በሐየሎም አረያ ጣልቃ ገብነት ተሰናከለ! ነገር ግን ግድያዉን ሳይፈጽሙ ላይተኙ ቃል የተገባቡት የጠቅላይ ሚኒስቴሩ ሳጥናኤሎች ወደ መኖሪያዉ ቤት በማምራት ተንኮላቸዉን ፈጸሙ በዚያዉ የሞት ድግስ ላይ አትለፊ ያላት የጥላሁን ገሰሰ ህይወት ግን እለቱን ተሻገረች ጥላሁን ለህክምና ከሐገር ሲወጣ በቁፋሮ የተገኘዉ የሐገራችን አንጡራ ሐብት ጥላሁንን አጅቦት ኮበለል።
ሞት ለወያኔ!

The post እውን ጥላሁን ገሠሠን በስለት ለመወጋት ያበቃው የ’ሆድ ይፍጀው’ ምስጢር ይህ ይሆን? appeared first on Zehabesha Amharic.

“ወልቃይት የትግራይ ነው! የአማራነት ጥያቄው በዚህ የማያቆምና ተጠናክሮ የሚቀጥል ከሆነ የማያዳግም እርምጃ እንወስዳለን” –አባይ ወልዱ

$
0
0

የህወሓት ከፍተኛ ባለስልጣናትና የአማራ ክልል ሹሞች በጎንደር ጎሃ ሄቴል ለሦስት ተከታታይ ቀናት ያደረጉት ድብቅ ስብሰባ ያለምንም ውጤት በፀብ ብቻ ተቋጨ፡፡ በህወሓቶችና በብአዴኖች መካከል የተካረረ ፍጥጫና ንትርክ ተከስቶ የነበረ መሆኑም ተደርሶበታል፡፡

abay weldu 2
(የአርበኞች ግንቦት 7 ድምፅ ሬድዮ) በጎንደር ከተማ ጎሃ ሆቴል ውስጥ ከጥር 28 እስከ የካቲት 1 2008 ዓ.ም በድብቅ በተካሄደው ስብሰባ ላይ የተገኙት የህወሓት ከፍተኛ ባለስልጣናት አባይ ፀሐዬ፣ ስብሃት ነጋ፣ ደብረ ፂዮን ገ/ሚካኤል፣ አባይ ወልዱ እና የትግራይ ክልል አስተዳደርና ፀጥታ ሹም ናቸው፡፡
ገዱ አንዳርጋቸው፣ አለምነው መኮንን እና መኳንንት /የአማራ ክልል ፀጥታ ሹም/ ደግሞ ከብአዴን ወገን የተገኙ የአማራ ክልል ሹማምንቶች ነበሩ፡፡


የህወሓት ከፍተኛ ባለስልጣናትና የህወሓት ዲቃላ የሆነው ብአዴን ባለስልጣናት በጎንደር ጎሃ ሆቴል ተሰብስበው የተነታረኩባቸው አጀንዳዎች ሁለት ሲሆኑ የወልቃይትን የአማራ ማንነት ጥያቄ እና ብረት ያነሱ የነፃነት ድርጅቶችን /በተለይም አርበኞች ግንቦት 7ን/ በሚመለከት ነው፡፡


የትጥቅ ትግል እያደረጉ የሚገኙ የነፃነት ድርጅቶችን በሚመለከት ህወሓቶች “ሰተት ብለው ከበረሃ ወደ ህዝቡ እንዲገቡ እያደረጋችኋቸው ነው…” በማለት ብአዴኖችን ወቅሰዋቸዋል፡፡


ከወልቃይት ህዝብ የአማራ ማንነት ጥያቄ ጋር በተያያዘ ደግሞ የትግራይ ክልል አስተዳዳሪና የህወሓት ሊቀ መንበር የሆነው አባይ ወልዱ እንዲህ ብሏል፡፡
“ወልቃይት የትግራይ ነው! የአማራነት ጥያቄው በዚህ የማያቆምና ተጠናክሮ የሚቀጥል ከሆነ የማያዳግም እርምጃ እንወስዳለን…!”


ቀጥሎም አባይ ወልዱ የአማራ ክልልን አስተዳዳሪ ገዱ አንዳርጋቸውን  “አንተ የአማራን ህዝብ የጦር መሳሪያ ያስታጠከው ሆነ ብለህ በትግራይ ላይ ጦርነት ለማወጅ ነው…” በማለት ተናግሮታል፡፡


ገዱ አንዳርጋቸውም በበኩሉ  “እኔ ህዝቡ በሀብቱ ገዝቶ ከጥንት ጀምሮ ታጥቆት የቆየውን ጦር መሳሪያ ህጋዊ ፈቃድ በመስጠት አፀናሁለት እንጂ ልክ እንዳንተ ከመንግስት ግምጃ ቤት አውጥቼ በገፍ አላስታጠቁትም፡፡ በትግራይ ህዝብ ላይ ጦርነት አወጅክ ላልከኝም የትግራይን ህዝብ ሰብስበህ በወልቃይት ህዝብ ላይ እርምጃ እንወስዳለን ብለህ በይፋ ጦርነት ያወጅከው አንተ ነህ፡፡” በማለት ለአባይ ወልዱ መልስ ሰጥቶታል፡፡ 


የጦር መሳሪያን በሚመለከት ደብረ ፂዮን ገ/ሚካኤል ገዱ አንዳርጋቸው የአማራን ህዝብ እንዳስታጠቀ ወቀሳ ሰንዝሯል፡፡ ደብረ ፂዮን ስለ ወልቃይት ህዝብ የአማራ ማንነት ጥያቄ የሚከተለውን በማለት ቁልጭ ያለ አቋሙን አስቀምጧል፡፡
“የወልቃይት ጉዳይ ክልል አንድን እንጂ ማንንም አይመለከተውም፤ ውሳኔውም ሊሆን የሚችለው የክልል አንድ ብቻና ብቻ ነው፡፡” 


ለዚህ የደብረ ፂዮን ንግግር ገዱ አንዳርጋቸው ሲመልስ
“እኛ ሄደን ኑ አንላቸውም፤ ከመጡ ግን የማንቀበልበት ምንም ምክንያት የለም፤ ደግሞም ውሳኔ ማስቀመጥ ያለበት ራሱ የወልቃይት ህዝብ ነው፡፡”


በመሆኑም በሁለቱ ክልሎች /በትግራይና አማራ/ አስተዳዳሪዎች ማለትም በአባይ ወልዱና ገዱ አንዳርጋቸው መካከል ስብሰባው ውስጥ የተካረረ ፍጥጫ ተከስቶ ነበር፡፡ 


ህወሓቶች ለገዱ አንዳርጋቸው ከባድ ማስጠንቀቂያ ሰጥተውታል፡፡


በአጠቃላይ በጎንደር ጎሃ ሆቴል ከጥር 28 እስከ የካቲት 1 2008 ዓ.ም በድብቅ የተካሄደው የህወሓቶችና የብአዴኖች ውይይት ያለምንም መግባባት በፀብ ብቻ ተጠናቋል፡፡

The post “ወልቃይት የትግራይ ነው! የአማራነት ጥያቄው በዚህ የማያቆምና ተጠናክሮ የሚቀጥል ከሆነ የማያዳግም እርምጃ እንወስዳለን” – አባይ ወልዱ appeared first on Zehabesha Amharic.

”አርጋኖን” እና ”ኦርጋን” ምን አገናኛቸው? ሰውን እንፈር፣እግዚአብሔርንም እንፍራ |የጉዳያችን ማስታወሻ

$
0
0

Abune Melekestedik Organ

ባለፈው ሰሞን ከወደ አሜሪካ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አውደ ምህረት ላይ ”በኦርጋን መዘመር ይቻላል”።የሚል እንግዳ ንግግር ተሰምቷል።የምንኖረው በምዕራቡ ዓለም ነው እና ማንም የመሰለውን ሃሳብ መስጠት ይችላል።ሆኖም ግን አሁንም የምንኖረው በምዕራቡ ዓለምም ነውና ማንም ግን ካለማንም ፍላጎት የግል ሃሳቡን በሌላ ላይ መጫን አይችልም። ስለ ኦርጋን የተነገረው  ከግል አስተያየትነት አያልፍም።ይህ ማለት ግን ትክክል ነው ማለት ግን አይደለም።ስንት የሚሰራ ሥራ ያላትን ቤተ ክርስቲያን ከስርዓቷ ውጭ የሆነ ተግባር እንድትፈፅም ለመጫን መሞከር መዘዙ ብዙ ነው።

 

አገረ አሜሪካ፣ ይሄው ሃሳብ የተሰነዘረባት አገር በርካታ የቤተ ክርስቲያኒቱ ሊቃውንት የሚገኙባት ነች።በተለይ በስደት የሚገኙ ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት ፓትርያሪክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆርዮስ ከሁለት አስርተ ዓመታት በላይ በስደት የሚገኙት አሁንም አሜሪካ ነው።አቡነ መርቆርዮስም ሆኑ በስደት የሚገኘው ሲኖዶስ ኦርጋን በየቤተ ክርስቲያን ይግባ የሚል ውሳኔ አላሳለፈም። በአገር ቤት የሚገኘው ሲኖዶስ ይልቁንም ከሃያ አመታት በፊት የቤተ ክርስቲያኒቱ የመዝሙር መሣርያዎች ምን ምን እንደሆኑ ለይቶ በቀኖና (ህገ ቤተክርስቲያንነት)  ወስኗል። በሁለቱ ማለትም በውጭ እና በአገር ቤት በሚገኙ አባቶቻችን መካከል ምንም አይነት የሃይማኖታዊ ዶግማዊም ሆነ ቀኖናዊ ልዩነት የለም።በሥርዓተ ቤተ ክርስቲያንም መሰረታዊ የሆነ የልዩነት ነጥብ አልተከሰተም።በእርግጥ በአንዳንድ አጥብያዎች ስርዓተ ቤተ ክርስቲያን ከሚፈቅደው ውጭ የሚታዩ ማዘንበሎች የአገር ቤቱንም ሆነ በውጭ በስደት የሚገኘውን ሲኖዶስ መገለጫ ሊሆኑ አይችሉም።

እውነታው እንግዲህ ይህ ሆኖ ሳለ በአሜሪካን አገር ስለ ኦርጋን በአውደ ምሕረት አንድ አባት ተናገሩ ተብሎ እንደ ስርዓት የተደነገገ ያክል የሚናገሩ  እና  አልፈው ተርፈውም ኦርጋንን ከአባ ዘጊዎርጊስ ድርሰት ጋር እያመሳሰሉ የሚፅፉ ግለሰቦች ሰው ይታዘበናል አለማለታቸው እየገረመኝ ነው።

ከሁሉ በፊት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ስርዓት ቀኖና በአስተያየት፣በአውደ ምህረት ላይ ንግግር ወይንም አንድ አባት ስለፃፈ ሕግ ይሆናል ማለት አይደለም።በአገራችን አንድ ባህታዊ ከቤተ ክርስቲያን ደጅ ላይ ከወገቡ በላይ እራቁቱን ሆኖ እራሱን በሰንሰለት እየገረፈ የሚናገረውን እንደ ሲኖዶስ ውሳኔ የሚወሰድበት አጋጣሚ መኖሩ በእራሱ አሳዛኝ ሆኖ ሳለ በውጭ የሚኖረው ምዕመን ሕግ እና ስርዓት ቤተ ክርስቲያኒቱ በማን እና እንዴት እንደምታወጣ የማያውቅ ይመስል ኦርጋን እና አርጋኖን እየተባለ ሲወናበድ ማየት አሳዛኝ ነው።አሁን አሁን  የአባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫን አርጋኖን የተሰኘውን እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምን የሚያመሰግነውን መፅሐፍ  ኦርጋን ከተባለው የሙዚቃ መሳርያ ጋር እያመሳሰሉ የሚፅፉ ሰዎች ለህሊና የሚከብድ ውሸት ሲዋሹ መመልከት ተለምዷል።

ይህንን ፅሁፍ እንድፅፍ ያነሳሳኝ ዛሬ በማኅበራዊ ድረ-ገፅ ላይ ያነበብኩት አንድ ፅሁፍ  በርካታ በተረታ ተረቶች  የተሞሉ ፅሁፎች ታጭቆበት ስለተመለከትኩ ነው።ለነገሩ ተረት ብቻ ሳይሆን ”አይን ያወጣ” በሚባል ደረጃ በውሸት የተሞላ ነው። ከፅሁፉ ውስጥ ሶስቱን ውሸቶች ብቻ ልጥቀስ:-

ውሸት አንድ – ”ኦርጋን የመዝሙር መምነሽነሽያ ነበር”

ውሸት ሁለት –”ኦርጋን ከአባይ ዳር ነው የተገኘው”

ውሸት ሶስት –”ቅዱስ ያሬድ ቅዱስ ኤፍሬም እና አባ ሕርያቆስ ኦርጋን ይጠቀሙ ነበር።ቅዱስ ያሬድ ኦርጋን ብሏል።” የሚሉ ይገኙበታል።

እዚህ ላይ ኦርጋን የተባለውን የሙዚቃ መሳርያ ከአሥራ አራተኛው ክ/ዘመን ኢትዮጵያዊው ሊቅ እና ቅዱስ አባ ዘጊዮርጊስ ዘጋስጫ ድርሰት የሆነው ”አርጋኖን” ጋር አንድ ነው የሚለው አባባል ሌላው አስቂኝ የማሞኛ ግን ደግሞ ምንም የማያውቁ ምዕመናንን ለማሳሳት የሚሞከረው ሙከራ  አደገኛ መሆኑን መግለጡ ተገቢ ነው።ለመሆኑ ኦርጋን የሙዚቃ መሳርያ ከሆነ አርጋኖን ምንድነው?

ስለ አርጋኖን እና አባ ጊዮርጊስ የተፃፈው ፅሁፍ እንዲህ ይነግረናል:-

”የአባ ዘጊዮርጊስ ዘጋስጫ የመጀመርያው ድርሰቱ አርጋኖን  የተሰኘውና በቅኔ ስለ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የሚያመሰግነው መጽሐፉ ነው፡፡ ስለ አርጋኖን ድርሰቱ ገድሉ በሚከተለው መንገድ ይገልጠዋል «ወሰመዮ በሠለስቱ አስማት ዘውእቶሙ አርጋኖነ ውዳሴ፣ ወመሰንቆ መዝሙር ወእንዚራ ስብሐት – በሦስት ስሞችም ሰየማቸው እነርሱም አርጋኖነ ውዳሴ፣ መሰንቆ መዝሙርና እንዚራ ስብሐት  ይባላሉ፡፡» ይህ አገላለጥ አንድ ነገር እንድናስተውል ያደርገናል፡፡ ይሄውም ስለ አርጋኖን መጽሐፍ ይዘት ነው፡፡ በገድሉ ላይ አርጋኖን መጽሐፍ አንድ ሆኖ ሦስት ክፍሎች ያሉት ነው፡፡ …. አርጋኖን ከሰኞ እስከ ዓርብ ላሉት ዕለታት ተከፋፍሎ የተዘጋጀ ሲሆን፣ እንዚራ ስብሐት ግን ከ«ሀ » እስከ «ፖ» ያሉትን ፊደላት በመክፈያነት በመጠቀም የተዘጋጀ ነው፡፡ ይህም አርጋኖንን አባ ጊዮርጊስ ሲያዘጋጀው አንድ ሆኖ በኋላ ግን በየክፍሉ እየተጻፈ የተባዛ ይመስላል፡፡እመቤታችን አርጋኖንን ስለ ወደደችለት ዚማት  በሚባለው ሀገር በነበረ ጊዜ «ከድርሰቶችህ ሁሉ እንደ አርጋኖን የምወደው የለም»  ብላዋለች፡፡ ዐፄ ዳዊትም ድርሰቱን በጣም ከመውደዱ የተነሣ በወርቅ ቀለም እንዳጻፈው ገድሉ ይገልጣል፡፡አባ ጊዮርጊስ የተወለደው በ1357 ዓም ነው።ወላጆቹ ልጅ ስለሌላቸው ዘወትር እያዘኑ ይኖሩ ነበር።አባ ጊዮርጊስ የተወለደው በቅዱስ ዑራኤል ብስራት መሆኑን ድርሳነ ዑራኤል ይተርክልናል።” +

ኢትዮጵያዊ ቅዱስ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ

ስለዚህ አርጋኖን ድርሰት ነው።ኦርጋን ደግሞ የሙዚቃ መሳርያ ነው። አሁን በ21ኛው ክ/ዘመን ሰዎች እንዲህ የማይገናኙ ነገሮችን አምታተው ፅፈው ሕዝብ ያታልላሉ ብሎ ማን ይጠብቃል? እየሆነ ያለው ግን ይህ ነው።

የኦርጋንን የሙዚቃ መሳርያ በተመለከተ ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ጋር አያይዞ የተሰጠው አስተያየት ጋር ተዛምዶ በማኅበራዊ ድረ-ገፅ የሚፃፉትን በተመለከተ መታወቅ ያለባቸው ሶስት ነጥቦችን አንስቼ ፅሁፌን ልደምድም።

1/ ቤተ ክርስቲያን መድረክ ላይ በሚሰጡ የግል ሃሳቦች ቀኖና አትቀንንም 

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን የምትመራባቸው መሰረታዊ መመርያዎች ምንጮች ሁለት ናቸው።አንዱ መሰረተ እምነቷ የሆነው ዶግማ ሲሆን ሁለተኛው አባቶች የሰሩላት ሥርዓቷ ወይንም ቀኖና ነው።

ዶግማን ሐዋርያውቅዱስ ጳውሎስም “ነገር ግን እኛ ብንሆን ወይም ከሰማይ መልአክ፥ ከሰበክንላችሁ ወንጌል የሚለይ ወንጌልን ቢሰብክላችሁ፥ የተረገመ ይሁን።አስቀድመን እንዳልን እንዲሁ አሁን ሁለተኛ እላለሁ፥ ከተቀበላችሁት የተለየውን ማንም ቢሰብክላችሁ የተረገመ ይሁን። ” በማለት እንዳወገዘው (ገላ. ፩፣ ፰ -፱) ማንም ማን ቢሆን የማይቀይረው መሰረተ ዕምነት ነው።ለምሳሌ የክርስቶስ ፍፁም አምላክነት ዶግማ ነው።ቀኖና  ግን የቤተ ክርስቲያኒቱን መሰረተ ዕምነት፣የመፅሐፍ ቅዱስ ትዕዛዛትን እና ቀደም ያሉ የቅዱሳን አበው ድንጋጌዎችን መሰረት አድርጎ የተሰራ ነው። ቀኖና በአውደ ምሕረት ላይ አንድ አባት ሃሳብ ስለሰጡ ”አይሻሻልም” አሁንም የቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔ ይፈልጋል።ቅዱስ ሲኖዶስ ደግሞ በመንፈስ ቅዱስ መሪነት ስለሚመራ የሚወስናቸው ውሳኔዎች በዘፈቀደ አይደለም።

በመሆኑም የኦርጋን ጉዳይ በውጭ ባለው ሲኖዶስም ሆነ በአገር ቤቱ ሲኖዶስ  የቤተ ክርስቲያን መሳርያ ነው የሚል ነገር የለም።ይልቁንም በአገር ቤት ሲኖዶስ በቤተ ክርስቲያኒቱ መንፈሳዊ መሳርያነት ተቀባይነት አላገኘም።በአገር ቤት እና በውጭ ባለው ሲኖዶስ መካከል ደግሞ የዶግማም ሆነ የቀኖና ልዩነት የለም።ይህንን በሁለቱም በኩል ያሉ አባቶች ደጋግመው ተናግረዋል።

2/ ኦርጋንን የሚከለክለው ማኅበረ ቅዱሳን ነውን ?

አሁን አሁን የተያዘው ፈሊጥ ኦርጋንን የሚከለክለው ማኅበረ ቅዱሳን ነው የሚል ነው።እንግዲህ ይህንን ለመረዳት በተራ ቁጥር አንድ ላይ ቤተ ክርስቲያኒቱ እንዴት ስርዓት እንደምታወጣ ከተመለከትን ከቤተ ክርስቲያን መዋቅር ስር በሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ ስር የሚገኘው ማኅበረ ቅዱሳን በምን ስልጣኑ ነው ስለ ቀኖና መቀነን ሥራ ገባ የተባለው።ደግሞስ በእዚህ ዘመን ስንት ያላመኑ ለማሳመን እንደመጣር በእየጭፈራ ቤት ማድመቅያ የሆነውን የሙዚቃ መሳርያ ከቤተ ክርስቲያን ካልገባ ብሎ ያዙኝ ልቀቁኝ ምን የሚሉት ፈሊጥ ነው? በእዚህም ሳብያ የቤተ ክርስቲያን ሌላ እራስ ምታት ለመሆን መሮጥ ምን አይነት አለመታደል ነው?

3/ ለምን ኦርጋን ተፈለገ?

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋኅዶ ቤተ ክርስቲያን ኦርጋን እንድትጠቀም የሚወተወትበት በተለይ በባእዳን በኩልም ጭምር የሚቀነቀነው ከሶስት ፍላጎቶች አንፃር ነው።

አንደኛው የቤተ ክርስቲያንም ሆነ የኢትዮጵያ መለያ እና ብቸኛ ባለቤት የሆነው የያሬዳዊ ዜማን ለማስጣል እና አገሪቱን ካለ አንዳች መለያ ማስቀረት፣

ሁለተኛ፣ በእዚህ ሳብያ የኢትዮጵያ ታሪክን በዋናነት የያዘችው ቤተ ክርስቲያንን መሰረታዊ መለያ መበረዝ የኢትዮጵያን ህልውና ማሽመድመድ ነው ከሚል እሳቤ አፍሪቃዊቷን ቤተ ክርስቲያን አውሮፓዊ ካባ ለማልበስ የሚደረግ እሩጫ እና

ሶሥተኛው ምክንያት በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ከፍተኛ መተራመስ ለመፍጠር የሚንቀሳቀሰው ለባዕዳን በማደር እና ጧት ማታ ባዕዳንን በማድነቅ የቤተ ክርስቲያንን እና አባቶች ያቆዩትን ስርዓት ለመናድ የሚጣጣረው እና  ባለፈው ሰኔ/2007 በርካታ ገፆች አትሞ በድብቅ የነበረውን ስራውን በይፋ ማውጣቱን የገለፀው ”የተሃድሶ እንቅስቃሴ” በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ልዩነት የመፍጠርያ ነጥብ ያገኘ መስሎት ስለሚያራግበው ነው።
ከእዚህ በታች ”አንድ አድርገን” ድረ-ገፅ ላይ የያረዳዊ የቤተ ክርስቲያናችንን ዜማ በባዕዳን መቀየር የሚመክሩትን አስመልክቶ ከሁለት ዓመት በፊት የወጣ ፅሁፍ የድርጊቱን እኩይ አላማ ስለሚያሳይ እንዳለ አቀርበዋለሁ።

ከአበው ከወረስናቸው በርካታ መንፈሳዊ ርስቶቻችን አንዱ መንፈሳዊው ዜማ ነው፡፡
ይህ መንፈሳዊ ዜማ አባቶቻችን ከእግዚአብሔር የተቀበሉትና ከእርሱ ጋር የተገናኙበትእኛም ተግተን ብንጠብቀው ወደ ሰማያዊ ኅብረት የምንነጠቅበት መሰላል ነው፡፡
መንፈሳዊው ዜማ በዓለም ካሉት ሀገራት ይልቅ ለኢትዮጵያ ተለይተው ከተሰጡሃብታት አንዱ ነው፡፡ኢትዮጵያ ከታላቁ አባት ከቅዱስ ያሬድ የተቀበለችው የዜማርስትም ጣዕሙን ለሚያውቀው በጦር መወጋትን እንኳን  ህመሙን ያስረሳ ነው (በቅዱስ ያሬድ ዜማ የተመሰጡት አፄ ገብረ መስቀል በጦር  የቅዱስ ያሬድ እግር ላይ በትረ መስቀላቸውን መትከላቸው እና  ሁለቱም ተመስጠው ሲነቁ መመልከታቸው) ፡፡ይህን የዜማ ርስት ግንበዚህ ዘመን አልሰጥም ብሎ እንደ ናቡቴ የሚጠብቅ አልተገኘም ፤ ንጉሥ አክዓብለናቡቴ ያቀረባቸውን ሁለት አማራጮችም በዘመናችን ትውልዱ በደስታ ተቀብሎትይገኛል፡፡
ለናቡቴ የቀረበው የመጀመሪያው ምርጫ ‹የአባቶችን ርስት ወስጄ ሌላ ርስትንልስጥህ › የሚል ነበር፡፡በዚህ ዘመንም ከአባታችሁ ከቅዱስ ያሬድየተቀበላችሁትን ዜማ ትታችሁ ሌላ ያሬዳዊ ያልሆነ ዜማን እናሰማችሁ ባዩ በዝቷል፡፡ይህንንም ጥሪ ተቀብሎ ያሬዳዊ ያልሆነን ዜማ ማድመጥና ማድነቅ የተለመደ ሆኗል፡፡
ሁለተኛው የናቡቴ ምርጫ ደግሞ ‹ገንዘብ ልስጥህ ርስትህን ስጠኝ› ነበር፡፡ይህንአይነቱንም መንገድ ዛሬ ብዙዎች የቀደመውን የዜማ ርስታችንን ለመጣላችን መንስኤነው፡፡፡፡የናቡቴና የእኛ ዘመን ነገር ልዩነቱ ናቡቴ በንጉሥተገድዶም እንኳን ርስቱን ሳይሰጥ የሞተ ሲሆን ይህ ትውልድ ደግሞ በራሱ ፍላጎትርስቱን እየሸጠና እየለወጠ መሆኑ ነው፡፡ 
ያሬዳዊ ዜማ የአንድ ወገን ባሕል ሳይሆን እግዚአብሔር በቀጥታ ለቤተ ክርስቲያን ዘኢትዮጵያ የሰጠው መንሳዊ ጸጋ ነው፡፡ያሬዳዊውን ዜማ ማጣጣልና መቃወም ቤተ ክርስቲያኒቱን መቃወም እንጂ የተወሰኑግለሰቦችን መቃወም አይደለም፡፡” +

በመጨረሻም ፅሁፌን ለመደምደም የምፈልገው በአንድ አረፍተ ነገር ነው።ሰውን መውደድ፣ አባትን መውደድ ወይንም ማድነቅ አንድ ነገር ነው።የሚወዱትን አባት የሚለውን ሁሉ የቤተ ክርስቲያኒቱ ቀኖና አስመስሎ ለምዕመናን ማቅረብ ግን የቤተ ክርስቲያንን ስርዓት አለማወቅ ነው።አርጋኖን እና ኦርጋን ምን አገናኛቸው? ሰውን እንፈር፣እግዚአብሔርንም እንፍራ!

ጉዳያችን GUDAYACHN
www.gudayachn.com

የካቲት 5/2008 ዓም  (ፈብሯሪ 13/2016)

ማጣቀሻ 

+  አንድ አድርገን ድረ-ገፅ 2006 ዓም
+  መፅሐፍ ቅዱስ
+  አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫ ልዩ መርሐ ግብር ግንቦት 10 እስከ 12 www.danielkibret.com

The post ”አርጋኖን” እና ”ኦርጋን” ምን አገናኛቸው? ሰውን እንፈር፣እግዚአብሔርንም እንፍራ | የጉዳያችን ማስታወሻ appeared first on Zehabesha Amharic.

በኦርጋን የመዘመሩ ጉዳይ |መዝሙርና የመዝሙር መሣሪያዎች

$
0
0

Yared kidus

ከዮሐንስ አፈወርቅ

 

ቅዱስ ጳውሎስ «ንቁ ፥ በሃይማኖት ቁሙ ፥ ጎልምሱ ጠንክሩ» ብሎ የሚመክረን መንፈሳዊ ንቃተ ሕሊናችንን ስሕተትና ኑፋቄን እንዲሁም የጥላቻን ወንጌል በሚሰብኩ በየዘመኑ የሚነሡ የሐሰት ሰዎች እንዳይዘናጋና በእነሱ ወጥመድ ውስጥ እንዳይጥሉን ነቅተን በሃይማኖት እንድንቆም ነው ። በቤተ ክርስቲያን መካከል ፍቅርና አንድነትን በማጥፋት ፥ ምእመናንን ከአባቶቻቸው ለማለያየት ምናምንቴ ሰዎችን በየጉባኤው እየላኩ አይሁድና ቢጽ ሐሳውያን ጉባኤውን እያወኩ ያስቸግሩት ስለ ነበር ንቁ ይላቸዋል። እንዲሁም በሀሰት ትምህርት ግራ እንዳይጋቡ በማሰብ በሃይማኖት ጸንተው ቁመው እንዲገኙ ቅዱስ ጳውሎስ “ንቁ” እያለ ምእመናንን ይመክራል ። በነቢያት ዘመን ነቢያተ ሀሰት የነቢያትን ትምህርት ያስተባብሉ እንደ ነበሩ ፣ በሐዋርያትም ዘመን ቢጽ ሐሳውያን የሐዋርያትን ትምህርት እየተቃወሙ ሕዝቡን ግራ ያጋቡ እንደ ነበር ፣ በዚህ ዘመንም ርቱዕ የሆነውን የቤ/ክ ትምህርትና ሥርዓት የሚቃወሙ ፣ የክርስቶስን ቤተ ክርስቲያን ለመክፈል ታጥቀው የተነሡ ግለሰቦች ራሳቸውን አደራጅተው ቤተ ክርስቲያንን የሚፈትኑበት ዘመን ስለ ሆነ ነቅተን ቤተ ክርስቲያንን ልጠብቅ ይገባል ።

መግቢያ

ንቁ ፥ በሃይማኖት ቁሙ ፥ ጎልምሱ ጠንክሩ» /1ቆሮ16 ፥13/

በመላው ዓለም የምትገኙ ኦርቶዶክሳውያን የተዋሕዶ ልጆች ክርስቲያኖች እንደ ምን አላችሁ ። የእግዚአብሔር ጸጋና ሰላም ፥ ፍቅርና ርኅራኄ ይብዛላችሁ ። ብዙዎቻችሁ የቤተ ክርስቲያኔ ነገር ያገባኛል ያሳስበኛልም ብላችሁ ርትዕት ስለ ሆነች ሃይማኖታችሁ በዚህ ሰዓት የቤተ ክርስቲያንን ጥሪ አክብራችሁ ስለ ተገኛችሁ የቤተ ክርስቲያን ራስ መድኃኔ ዓለም ክርስቶስ ያክብራችሁ ።

ቅዱስ ጳውሎስ «ንቁ ፥ በሃይማኖት ቁሙ ፥ ጎልምሱ ጠንክሩ» ብሎ የሚመክረን መንፈሳዊ ንቃተ ሕሊናችንን ስሕተትና ኑፋቄን እንዲሁም የጥላቻን ወንጌል በሚሰብኩ በየዘመኑ የሚነሡ የሐሰት ሰዎች እንዳይዘናጋና በእነሱ ወጥመድ ውስጥ እንዳይጥሉን ነቅተን በሃይማኖት እንድንቆም ነው ። በቤተ ክርስቲያን መካከል ፍቅርና አንድነትን በማጥፋት ፥ ምእመናንን ከአባቶቻቸው ለማለያየት ምናምንቴ ሰዎችን በየጉባኤው እየላኩ አይሁድና ቢጽ ሐሳውያን ጉባኤውን እያወኩ ያስቸግሩት ስለ ነበር ንቁ ይላቸዋል። እንዲሁም በሀሰት ትምህርት ግራ እንዳይጋቡ በማሰብ በሃይማኖት ጸንተው ቁመው እንዲገኙ ቅዱስ ጳውሎስ “ንቁ” እያለ ምእመናንን ይመክራል ። በነቢያት ዘመን ነቢያተ ሀሰት የነቢያትን ትምህርት ያስተባብሉ እንደ ነበሩ ፣ በሐዋርያትም ዘመን ቢጽ ሐሳውያን የሐዋርያትን ትምህርት እየተቃወሙ ሕዝቡን ግራ ያጋቡ እንደ ነበር ፣ በዚህ ዘመንም ርቱዕ የሆነውን የቤ/ክ ትምህርትና ሥርዓት የሚቃወሙ ፣ የክርስቶስን ቤተ ክርስቲያን ለመክፈል ታጥቀው የተነሡ ግለሰቦች ራሳቸውን አደራጅተው ቤተ ክርስቲያንን የሚፈትኑበት ዘመን ስለ ሆነ ነቅተን ቤተ ክርስቲያንን ልጠብቅ ይገባል ።

እኔ ዛሬ ይህንን መልእክት እንዳቀርብ ያስፈለገበት ምክያት ፣ በቅርቡ እንደ አዲስ ነገር ተደርጎ ራሱን «ማኅበረ ቅዱሳን» (ማቅ) ብሎ በሚጠራው ድርጅት  በተሰማሩ  የሐራ ጥቃ ሰባኪዎች አማካይነት የአርጋኖን ነገር በማንሣት ሕዝበ ክርስቲያኑን በውጭ አገር የሚገኙ አባቶች ኦርጋን ወደ የቤተ ክርስቲያን በማስገባት የቤተ ክርቲያናችንን ሃይማኖት እንዲለወጥ እያደረጉ ነው በማለት ፣ ቴሌ ኮንፈረንስ በማድረግ ሕዝቡን ግራ በማጋባት ላይ ስለሚገኙ ፣ ይልቁንም የታላቁን ሊቅ የብፁዕ አቡነ መልከጼዴቅን ስም በማጥፋት የሐሰት ከሳሾች ሁነው ስለ ተገኙ ፣ ሕዝበ ክርስቲያኑ እውነቱን እንዲረዳ ለማድረግ ነው ።

ምእመናን ! ይህ ዘመቻ የማኅበረ ቅዱሳን(ማቅ) መልእክተኞች ሁለተኛው ዙር ዘመቻ ነው ። በመጀመርያው ዘመቻ በውጭ ሀገር ያለችውን ቤተ ክርስቲያን በመከፋፈልና በሀገር ውስጥና በሀገር ውጭ የሚገኙ አባቶችን በማወጋገዝ ተጠናቆ ነበር ። የመጀመሪያውን ዘመቻ ከዛሬ አሥር ዓመት በፊት 2003 እኤ ጀምሮ አካሂዶ ነበር ። አላማውም በሰሜን አሜሪካ በማኅበሩ የሚመሩ አብያተ ክርስቲያናትን ለመመሥረት ሲሆን ዘመቻውን ያጧጧፈው በውጭ ሀገር ያሉ አንድ አንድ አብያተ ክርስቲያናትን በኦርጋን መዘመራቸው ትክክል አይደለም ፤ በውጭ አገር ባለቺው ቤተ ክርስቲያንም የሚያስተምሩ መምህራን መናፍቃን ናቸው ፣ ሲኖዶስ በአዲስ አበባ እንጂ በአሜሪካ የለም ፣ ወዘተ እያሉ ነበር የዘመቱት ። በመጨረሻም በሀገር ቤት ያሉትን አባቶችና በውጭ ሀገር ያሉትን አባቶች ለማወጋገዝ እስኪችል ድረስ የተሳሳተ መረጃ አዲስ አበባ ላሉት አባቶች በማቀበል ትልቅ ሚና ተጫውቶ ችግሩ  በልዩነት ቀጠለ ። ድርጅቱ የአዲስ አበባውን ሲኖዶስም አመራር አይቀበልም ። ነገር ግን በስደት የሚገኙትን አባቶች የሚዋጋው «እናት ቤተ ክርስቲያን» በሚል ስም ነው ። ግቡም የኢኦተቤክ  አስተዳዳራዊ ሥልጣን  መንጠቅ ነው።

mahibere-kidusan-logoይሁን እንጂ “ማቅ” ከአራት ዓመት በፊት በአትላንታ ባደረገው ስብሰባ ከአሁን በኋላ በውጭ አገር የሚገኘውን ሲኖዶስና አባቶች መቃወሙ በሕዝብ ዘንድ እያስጠላን  ስለመጣ አንደኛ የራሳችንን ቤተ ክርስቲያን እናጠናክር ። ሁለተኛ በሌሎችም ቤተ ክርስቲያን ውስጥ በመግባት የአባልነት ክፍያ እየከፈልን ከሰበካ ጉባኤው /ቦርድ/ ውስጥ ገብተን በመከፋፈል ሕዝቡን ግራ በመለያየት ፥ ከቻልን ቤተ ክርስቲያኑን እንረከበዋልን ካልቻልን ሰላም እንነሳቸዋለን ብሎ የሰልፍ ስልቱን ቀይሶ ነበር ።

ከዛሬ ዓመት በፊት ደግሞ ሲያትል ላይ  አዲስ እቅድ በመንደፍ አሁን በየቤተ ክርስቲያኑ ውስጥ ገብተው  የሚታገሉ ተቃዋሚዎችን አፍረተናል ፤ በጀት በጅተን በውጭ ሀገር የሚያገለግሉትን ጳጳሳትና ካህናት የሚቃወም ንቅናቄ በመፍጠር ሕዝባቸው ዘንድ ተሰሚነት እንዳያገኙ በማድረግ ሕዝቡን አስደንግጠን ወደኛ እንዲመጣ ማድረግ አለብን ብለው ይኸውና በዓመቱ ድርጅቱ  በገንዘብ የገዛቸውን ምናምንቴዎች አዝምቶ በመዋጋት ላይ ይገኛል ።

በመሆኑም ጦርነቱንም ለማፋፋም በዋናነት ምክንያት ያደረገው አረጋዊው አባት  በሎሳንጀለስ ጥምቀት ላይ ስለ አርጋኖን ተጠይቀው የሰጡትን ማብራሪያ ነው ። ስለዚህ አርጋኖንን አስመልክቶ የተነሣውን ጥያቄ ምክንያት በማድረግ ጠቅላላ ስለ መዝሙር መሣሪያዎች ማብራሪያ ለመስጠት «መዝሙርና የመዝሙር መሣሪያዎች» በሚል ርእስ ይህ ጥናታዊ ጽሑፍ ተዘጋጀ ።

ይህ ጥናታዊ ጽሑፍ አርጋኖን ለሚቃወሙ የቢጽ ሐሳው ማቅ አባላት መልስ ለመስጠትበ2003 ለመጀመሪያ ጊዜ ተዘጋጅቶ የቅዱስ ሲኖዶስ ልሳን በሆነው ነጸንራቅ መጽሔት ላይ በ2005 የተሰራጨ ሲሆን ፥ እንደ ገና ከ10 ዓመታት በኋላ እንዳዲስ ጥያቄውን ስላነሡ የመጀመርያው ጽሑፍ ተሻሽሎ በ2016 እኤ እንደ ገና ለንባብ ቀረበ ።

  • መዝሙርና የመዝሙር መሣሪያዎች

በዚህ ርእስ ስለ ዜማ ስልት ስለ መዝሙር እና የመዝሙር መሣሪያዎች ስለ ቅዱስ ያሬድ መሠረታውያን የዜማ ስልቶችና ትርጓሜ ጠቅለል አድርጌ ለማብራራት ጥረት አደርጋለሁ ።

  • ስለ ዜማ ስልት

yaredዜማ ማለት ስልት ያለው ጩኸት ወይም በሥርዓት በደምብ የሚሰማ ድምጽ ፥ ሰሚውን የሚማርክ የሚመስጥ ፥ ለስሜት ትርጉም የሚሰጥ ድምጽ ማለት ነው ። ቀሌምንጦስ እና አርጋኖን የሚባሉት የቤተ ክርስቲያን መጻሕፍት ፥ ዜማ ከሰው አንደበት የሚወጣ ብቻ ሳይሆን ከወፎች የምንሰማው መልካም ድምጽም ሆነ ከዜማ መሣሪያዎች ቅኝት የምንሰማው ድምጽ ዜማ እንደ ሆነ ፥ ዜማም እንዳለው ፥ ዜማም እንደሚባል ይናገራሉ ። የመጻሕፍቱ ቃል በግእዝ እንዲህ ይላል “አእዋፍ ዘሠናይ ዜማሆሙ ይሴብሕዎ በሠናይ ዜማ ወማኅሌት” ይህም ማለት “ዜማቸው ያማረ ወፎች በመልካም ዜማቸው ያመሰግኑታል” ማለት ነው ። እንዲሁም “ኅብረተ ዜማ ግእዝ እዝል ወዓራራይ ፥ ዝብጠተ መሰንቆ ወእንዚራ እለ ቦሙ ሠናይ ዜማ” ይላል ። ሲተረጐም “በግእዝ በእዝል በዓራራይ የዜማዎች ኅብረት ዜማቸው መልካም ከሆነ ከመሰንቆና ከእንዚራ መደርደር (መመታት) ጋር ያመሰግኑታል” ማለት ነው ። (ያሬድናዜማው)

ከዚህ በላይ እንዳየነው መልክና ስልት ያለው ጩኸት ሁሉ ዜማ አለው ፥ ዜማ ነው ፥ ዜማ ይባላል ።

  • የዜማ ክፍሎች

ዜማን በሁለት ክፍል ማየት እንችላለን።

  • መንፈሳዊ ዜማ
  • ሕዝባዊ ዓለማዊ ዜማ
  • መንፈሳዊ ዜማ

መንፈሳዊ ዜማ የምንለው በቤተ እግዚአብሔር እና እንዲሁም በዓበይት በዓላት በሕዝብ አደባባይ በእውነተኞች የዜማ ሊቃውንት በቅዱስ ያሬድ ደቀ መዛሙርት በድጓ በአቋቋም መምህራን የሚቀርብ እውነተኛው ያሬዳዊ የምስጋና ዜማ ነው ። /መዝ 5 ፥ 3 ። መዝ 62 ፥ 6 ። መዝ 11 8 ፥ 62/

  • ሕዝባዊ ዜማ

ስልቱ የተወሰደው ምንጩና መገኛው መንፈሳዊ ዜማ ነው ። ነገር ግን ስሙ እንደሚያመለክተው የሚውለው እንደ ሕዝቡ ባሕልና ሥርዓት ለዘፈንና ለልቅሶ ለዋይታ ለሽለላ (ለጃሎታ) ለቅሮሮሽ (ቅርርቶ) ወዘተ ነው ። ሕዝቡ የእግዚአብሔር ሕዝብ የሆነ እንደ ሆነ “ሆ!” እያለም በሆታ ይዘምራል ። እግዚአብሔርንም ያመልክበታል ። ለምሳሌ በሀገራችን “ሆ! ነይ ነይ እምዬ ማርያም ፤ በወት ግባ በወት ያገራችን ታቦት ፤ ኤልያስ በሠረገላ ፤ ኧረሰይ አማኑኤል፤…” ሌሎችም በሕዝብ ዜማ የሚቀርቡ የበዓል የሕዝብ ዜማዎች ናቸው ። ዛሬ ዛሬ ግን ዳብሮና ሰፍቶ በልዩ ልዩ ሕዝባውያን ዘማሪዎች ተቀናጅቶ ሲዘመር ይታያል ። ደስ የሚያሰኝ ነው ።

ሕዝብ ከእግዚአብሔር የተለየ ከሆነ ግን በሕይወቱ ስለ አጋጠመው ገጠመኝ ስለ ሥጋ ፍላጎቱ ስለ ምኞቱ ይዘፍንበታል ። በሌላም መልኩ ደግሞ ስለ ሀገሩ ስለ ወገኑ ያለውን ፍቅር ይገልጽበታል ።

መንፈሳዊውም ሆነ ሕዝባዊው ዜማ በአንድ ነገር ይገናኛል ። መንፈሳዊው ዜማ የሥጋንም የመንፈስንም ጉድለትና ክብር ፣ ሞትና ሕይወት ፣ ጽድቅና ኲነኔ ፣ ሌላም ሌላም ሲገልጽ ። ዓለማዊው ዜማ በበኩሉ የዓለሙን ጉድለትና ምኞት ይገልጻል ። ሁለቱም የሰውን የውስጥ ስሜት በመግለጽ አንድ ይሆናሉ ። ይዞታቸውና መልእክታቸው ግን ፍጹም የተለያየ ነው ።

ከሰው ልጅ ስሜት አንጻር ዜማ ሲታይ ከገነት የተለየ ከእግዚአብሔር የራቀ የሰው ልጅ በመቆዘም በማንጐራጐር በደሉን ማሰብ ማንነቱን ማስታወስ ከእግዚአብሔር እርዳታ መጠየቅ ፥ ብሶቱንም መግለጽ የቻለበት መንገድ ነው ። ከዚያ በፊት ግን (ከስህተት በፊት) መታከትን ድካምን በማያስከትል የምስጋና ቃል ሕይወቱ የተመላ ነበር ። ከውድቀት በኋላ ግን እርዳታ ፈላጊ ሆነ ። ጩኸቱን እንደ ሀገሩ ልማድ እና እንደ ጸጋው መጠን በልዩ ልዩ ሥነ ዜማ ማቅረብ ጀመረ ። የተፈረደበትን ፍርድም ሆነ የተፈረደለትን በጐ ነገር  በዜማ መግለጽ ጀመረ ። የዜማ መጻሕፍትም ዋና ማዕከላዊ አስተምህሮ የሰው ልጅ ሞትና ሕይወት ፣ የእግዚአብሔር ፍርድና ምሕረት ናቸው ።

  • ያሬዳዊ ዜማ

ቅዱስ ያሬድ በመንፈስ ቅዱስ ጸጋ የተማወቀ ፥ በቅዱሳት መጻሕፍት እውቀት የተራቀቀ ሊቅ ፣ በጸጋ እግዚአብሔር የተቃኘ ፥ በሥነ መለኮት አስተምህሮው የላቀ ፥ ምጡቅ ሰው እንደ ነበር ድርሰቶቹና የቤተ ክርስቲያን ታሪክም ምስክሮች ናቸው ። ቅዱስ ያሬድ ኅዳር 5 ቀን 534 ዓ.ም ከሰማይ ድምጽ ሰምቶ ሀብተ ዜማ ተሰጥቶት አፄ ገብረ መስቀል በመስከረም 25 ቀን 534 ዓ.ም ነግሠው እርሱ በኅዳር ከጣዕሙ ብዛት የተነሣ አጥንት የሚያለመልም ዜማ ደርሷል ።

ጥቅስ በግእዝ፤ “ወሰምዐ በህየ ቃለ እንዚራ ወቃለ አርጋኖን ወቃለ መሰናቅው እንዘ ይሴብሕዎ ወይዌድስዎ ወየአኲትዎ ለፈጣሬ ሰማያት ወምድር በስብሐት ወበማኅሌት በቅኔ ወበልዑል ዜማ ነግሀ ወሠርከ ይሴብሕዎ ለንጉሥ ዐቢይ በዓውደ መንበሩ ቅዱስ…አነ እነግረከ በዘትሌቡ ጸውዕ ስሞ ሐዲሰ ለእግዚአብሔር ዘውእቱ ኢየሱስ ክርስቶስ ወትነስእ ማኅሌተ እም ዕሥራ ወአርባዕቱ ካህናተ ሰማይ በበዜማሁ ወይቤ ጐስዐ ልብየ…”

ትርጉም በአማርኛ፤ በዚያም የእንዚራን ፣ የአርጋኖን ፣ የመሰንቆን ድምጽን እንዲሁም ሰማይንና ምድርን የፈጠረ ትልቁን ንጉሥ እግዚአብሔርን ጧትና ማታ በስብሐትና በማኅሌት በቅኔ ጧትና በሰርክ ከፍ ባለ ዜማ ካህናተ ሰማይ መላእክት በተቀደሰ ዙፋኑ ዙሪያ ሲያመሰግኑ ሰማ…እንግዲያውስ እኔ የምታስተውልበትን እነግርሃለሁ ። የእግዚአብሔርን አዲስ ስም ጥራ ። ይኸውም ኢየሱስ ክርስቶስ ነው ። ከሃያ አራቱ ካህናተ ሰማይም በየአይነቱ ዜማ ያለውን ማኅሌት ትማራለህ የሚል ቃል ሰማ … ልቤ መልካም ነገርን አውጥቶ ተናገረ።” ብሎ ተናገረ ፤ የዜማ ሐብትም ተሰጠው ። (ጥንታዊ ሥርዓተ ማኅሌት ዘአቡነ ያሬድ ሊቅ ገጽ 23-24) ተብሎ እንደተጻፈ።

  • ሦስቱ የቅዱስ ያሬድ የዜማ ስልቶች

ግእዝ፦ ግዕዝ ማለት የዜማ መጀመሪያ የመጀመሪያ ዜማ አንደኛ ቀዳሚ ማለት ነው

ዕዝል፦ ዕዝል ማለት በግዕዝ ላይ ታዝሎ ተደርቦ የሚዜም የሚዘመር ከባድ የበዓል የደስታ ቀን ዜማ ማለት ነው።

ዓራራይ፦ አራራይ የሚያራራ፤ ልብ የሚመስጥ ትዝታ ተመስጦ የሚያስከትል ዜማ ማለት ነው።

ቅዱስ ያሬድ በእነዚህ የዜማ ስልቶች ላይ ተመሥርቶ ስለ እግዚአብሔር መኖር ፣ ስለ ፍጥረተ ዓለም ፣ ስለ ምሥጢረ ሥላሴ ፣ ስለ ምሥጢረ ሥጋዌ በአጠቃላይ ትምህርተ ሃይማኖትን ፣ ነገረ መለኮትን፣ ክብረ ቅዱሳንን መሠረት አድርጐ በሰፊው ዘምሯል ። አምስቱ የቅዱስ ያሬድ የዜማ መጻሕፍትም (ድጓ ፥ ጾመ ድጓ ፥ ምዕራፍ ፥ ዝማሬ  ፥ መዋሥዕት) የሚያረጋግጡት ይህንኑ ነው ።

  • የመዝሙር መሣሪያዎች ከየት መጡ?

1/ መለከት፦ ከቀንድ፣ ከብረት እና ከብር የሚሠራ የእግዚአብሔር ጉባኤ መጥሪያ ፥ ለመዘመሪያም የሚያገለግል መሣሪያ ነው ። አንዳንድ ጊዜ ቀንደ መለከት ይባላል ፣ ከቀንድ መሠራቱን ያመለክታል ። መለከትን ለመጀመሪያ ጊዜ የሠሩት የቃየል ልጆች ናቸው ። የተጠቀሙበትም መጀመርያ እነርሱ ናቸው ። በመጽሐፍ ቅዱስ እንደምናነበው ለመጀመሪያ ጊዜ ከተማ የቆረቆሩ ፥ የተፈጥሮ ሕግን ሽረው ከአንድ በላይ ሚስት ማግባትን የጀመሩ ፥ የነፍሰ ገዳዩ እና የቀበዝባዛው ፥ የእግዚአብሔር ልጆች ከመባል የሰው ልጆች ለመባል ያበቃው የእርጉሙ የቃየል ልጆች ናቸው ። መለከትን የሠሩት በከተማቸው ሊዘፍኑበት ሊያንጐራጉሩበት ነበር ። ከእግዚአበሔር የተለየች በሕገ ተፈጥሮ /ሕሊና/ ላይ ያመጸች ፥ ሞት የተፈረደባት ሕይወታቸውን ለማባበል የዜማ ዕቃ ልዩ ልዩ ነገሮችን እየቀጠቀጡ ይሠሩ ነበር ።  ምሥጢሩ ግን በደለኛው ማንነታቸው /ሕይወታቸው/ እርዳታ እየፈለገ ሰላም አጥቶ መቆዘምና ማንጐራጐር መጀመሩን ያመለክታል ። ዛሬም አንድ ሰው በሠራው ኃጢአት ምክንያት የሕሊና ሰላም እንደሚያጣ እና ሁከት እንደሚነግሥበት ። እነርሱም በአንደበታቸው ጩኸት ሊወጣላቸው ያቃታቸውን ከልባቸው የተረፈውን የውስጥ ጩኸት በመሣሪያ እየታገዘ ይወጣ ጀመር ።

እግዚአብሔር ሰውን ለምስጋና እንጂ ለዘፈን አልፈጠረውም ፤ የሚያዝነውም ሆነ የሚደሰተው የሚዘምረውም ሆነ የሚዘፍነው ሰው ያለው አንድ ስሜት ብቻ ነው ። ሰው በቅጽበት ልዩነት ሊሆን ይችላል እንጂ በአንድ ጊዜ ደስታ እና ኃዘን አይሰማውም ። ስሜቱ አንድ ብቻ ስለ ሆነ ግን እንደ ሁኔታው ስሜቱ ይለዋወጣል ። ሰይጣን የሰው ልጆችን የተፈጥሮ ጸጋ የሆነውን የምስጋና ስሜት በመለወጥ ለብሶት ጩኸትና ለዘፈን እንዲጠቀሙበት ገፋፋቸው ። ለእግዚአብሔር ክብር እንዳይዘምሩ በኃጢአት አውሮ  ወንዱ ስለ ሴቶች ሴቶቹም ስለ ወንድ ማቀንቀን ጀመሩ ። የእግዚአብሔር ፍቅርም ክብርም ከነሱ ራቀ ። በመሆኑም በዓለም የሰው ልጆችና የእግዚአብሔር ልጆች ተብለው በሁለት ሲከፈሉ መለከትን ሰርተው ይጠቀሙ የነበሩት የሰው ልጆች የተባሉ የቃየል ልጆች ነበሩ ። /ዘፍ 4 ፥ 21 ዘፍ 2 ፥ 6/

በኋላ ግን መለከት ለመንፈሳዊ አገልግሎት ዋለ ። የእግዚአብሔር ክብር ታወጀበት ። የቃየል ልጆችም የእግዚአብሔር ፍጥረቶች ናቸው ። አእምሮንም ሰጥቶ  የፈጠራቸው እግዚአብሔር ነው ። ለሰይጣን የራሱ የሆነ ንብረት የለውምና የደከሙበት ዕቃ ለበጐ ዋለ ። ሰይጣን በእግዚአብሔር ፍጥረት በደል ቢሠራ ያሳዝናል እንጂ ፥ እግዚአብሔር በኃጢአት አልገዛልህም ያሉትን ቢገዛቸው የሚያስገርም አይደለም ፤ ንብረቱ ናቸውና ።

የመለከት አገልገሎት የተገለጸባቸው የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች ከዚህ የሚከተሉት ናቸው ። ዘኍ 10 ፥ 1-10 ። ኢያ 6 ፥ 20 ። 2ዜና 5 ፥ 12-13 ። 2ሳሙ 6 ፥ 15 ። 1ዜና 15 ፥ 28 ።

2/ በገና፦ አሥር አውታር ያለው የዜማ ዕቃ ነው ። ለመጀመሪያ ጊዜ የሠሩት የተጠቀሙበትም እንደ መለከት ዘፋኞች የቃየል ልጆች ናቸው ። ዘፍ 4 ፥ 21 ።

ለዘፈን ብለው የሠሩት የሰው ልጆች /የሥጋና  የደም ሥራ የሚሠሩ/ ናቸውና ዘፈኑበት ። /ዘፍ 6 ፥ 2/

የእግዚአብሔር ልጆች ደግሞ ለመዝሙር ለምስጋና ተጠቀሙበት ፣ እኛም እንጠቀምበታለን ። ቁም ነገሩ ከሠሪዎቹና ከመሣሪያው ላይ ሳይሆን ከአጠቃቀሙ ላይ ነው ። ልዩ የመዝሙር መሣሪያም ሆነ ። ስለ በገና የሚናገሩ የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች ። ዘፍ 4 ፥ 21 ።1ሳሙ 16 ፥ 16-23 ። 1ዜና 15 ፥ 21 ። መዝ 32 ፥ 2 ። ራእይ 5 ፥ 8 ።

3/ ክራር፦ የበገና ዓይነት የዜማ ዕቃ ነው ። የዘመናችን ክራር አምስት ወይም ስድስት የጅማት አውታሮች አሉት ። ክራርን በበገና ዓይን ካላየነው በቀር በክራር ሲዘመር እንደ ነበር ክራር የመዝሙር መሣሪያ  እንደ ሆነ መጽሐፍ ቅዱስ  በመዝሙር መሳሪያነት ጠቅሶት አናገኝም ። በስም ግን ጠርቶት ይገኛል ። ናቡከደነጾር ጣዖቱን ካሳጀበባቸው መሣሪያዎች አንዱ ክራር እንደ እንደ ነበረ በትንቢተ ዳንኤል ተጠቅሶ እናነባለን ። 3 ፥ 5-7 ።

ቅዱስ ጳውሎስ ስለ ልሳን ሲናገር ሕይወት የሌላቸው መሣሪያዎች ሲቃኙ እንደ ቅኝታቸው ስሜት የሚሰጥ ድምጽ ይሰጣሉ ። እንዴት እናንተ በልሳን እንናገራለን እያላችሁ ትርጉም የለሽ ነገር ትናገራላችሁ ብሎ  የቆሮንቶስን ቤተ ክርስቲያን ግብዞች ባስተማረበት ክፍል ለምሳሌ ከጠቀሳቸው መሣሪያዎች ክራርና  ዋሽንት ይገኙበታል ። 1ቆሮ 10 ፥ 7 ።

በተጨማሪም ክራር በብሉይ ኪዳንም ሆነ በአዲስ ኪዳን /የአሁኑን ዘመን አይጨምርም/ የጐላ የመዝሙር ቦታ  ተሰጥቶት አልተነበበም ። ይሁን እንጂ በክራር መዘመሩ በደል አይደለም ። ቤተ ክርስቲያን ግን ባትለየውም እውቅና አልሰጠችውም ። በአሜሪካ ያሉት አባቶች ጉባኤ ቅዱስ ሲኖዶስም ሆነ በኢትዮጵያ ያሉት አባቶች ጉባኤ ቅዱስ ሲኖዶስ በውሳኔው ውስጥ በተራ ቍጥር አልጠቀሰውም ።

4/ ዋሽንት፦እንደ ክራር ናቡከደነጾር ጣዖት ካሳጀበባቸው መሣሪያዎች አንዱ ነው። ዳን 3 ፥ 5-7። 1ቆሮ 14 ፥ 7 ።

ይሁን እንጂ ለሰይጣን ንብረት ስለሌለው እንደ አጠቃቀሙ ስለ ሆነ ለእግዚአብሔር ክብር መዋሉ ባይነቅፍም ቤተ ክርስቲያን ግን እውቅና ሰጥታ በዚህ አመስግኑ ብላ በውሳኔ አላስተላለፈችም ። ዋሽንት በሀገራችን ባሕል የሕዝብ መጫወቻ ነው ። በመሆኑም የከበረ ዕቃ ነው ።

5/ መቋሚያ፦ በቅዱስ ያሬድ ለመጀመሪያ ጊዜ ለመዝሙር የዋለ የዜማ ማሣሪያ ፥ የመዝሙር መሳሪያ ነው ። የሚሠራውም ቀጥ ካለ እንጨት ሁኖ ጫፉ ላይ የቀንድ የብር የነሐስ የብረት የእንጨት መያዣ (መደገፊያ) ያለው ነው ። በመጽሐፍ ቅዱስ አልተጠቀሰም እግዚአብሔር በየዘመናቱ አዳዲስ ጸጋ ለሰዎች ስለሚሰጥ ለአባታችን ለቅዱስ ያሬድ የሰጠው ልዩ የማመስገኛ ዘንግ ነው ። መጽሐፍ ቅዱስ በመቋሚያ አመስግኑት አላለም ብለን የእግዚአብሔርን ጸጋ ልንቃወም አንችልም በየዘመኑ አዲስ ጸጋ የሚሰጥ እግዚአብሔር ነውና ። ቅዱስ ያሬድ በዚህ ዘመን ተነሥቶ ቢሆን ግን መቋሚያህን አስቀምጥ የሚሉ ከሳሾች በተነሡበት ነበር ።

6/ ከበሮ፦ፍጹም ለእግዚአብሔር ክብር የዋለ የመዝሙር ዕቃ ነው። ለድል ቀን መታሰቢያ ይመታ ነበር።ዘጸ 5 ፥ 20

ለእግዚአብሔር ክብር መዝሙር የሚቀርብበት መሣሪያ ነው ። መዝ 149 ፥ 4 ።

ለታቦት ክብር ይዘመርበታል ። 1ሳሙ 18 ፥ 6 ። 2ሳሙ 6 ፥ 5 ።

በአንጻሩም የእግዚአብሔር ሕዝብ እግዚአብሔርን ሲያመሰግንበትን ዓለም ደግሞ ወስዳ ትዘፍንበታለች ። ያ ግን የከበሮን አገልግሎት ክብር አይቀንሰውም ።

7/ ጸናጽል፦ ሁለት ዓይነት ጸናጽል አለ ። አንደኛው የማጨብጨቢያ ጸናጽል ናቁስ ይባላል ። እንደ መረዋ ያለ ነው ይላሉ አበው ። አሁን እኛ ዛሬ አንጠቀምበትም ፣ መሣሪያውም የለንም ። ሁለተኛው አሁን የምንጠቀምበት ዓይነት ጸናጽል ነው ። ከነሐስ ከብር ከወርቅ ይሠራል ። ጸናጽል የተቀደሰ የመዝሙር መሣሪያ ነው ። 2ሳሙ 6 ፥ 5 ። መዝ 150 ፥ 5 ። 1ዜና 13 ፥ 8 ። 2ዜና 5 ፥ 13 ። 1ቆሮ 13 ፥ 1 ።

8/ መሰንቆ፦ “ሰንቀወ” ሰነቃ ፥ ሞዘቀ ፥ መታ ፥ አስጮኸ ፥ ከረከረ ከመሣሪያው ጋር ጮኸ ፥ አዜመ ፥ ዘመረ ፥ ገጠመ ፥ አጉረመረመ ከሚለው የግእዝ ቃል የመጣ ነው ። ግሩም የሆነ የመዝሙር መሣሪያ ነው ። ኢሳ 5 ፥ 12 ። ኢዮ 21 ፥ 12 ። ኢሳ 23 ፥ 16 ። ሲራ 22 ፥ 6  ። ዮዲ 16 ፥ 1 ። መዝ ። 150 ።

9/ እንዚራ፦ “አንዘረ” መታ ከሚለው የግእዝ ቃል የወጣ ይመስላል ። ግን አንዳንድ መጻሕፍት የሚመታ መሣሪያ ሳይሆን በእስትንፋስ የሚነፋ መሣሪያ እንደ ሆነ ያመለክታሉ ። የእንዚራን ትክክለኛ መልክ እስከ አሁን ማግኘት አልተቻለም ። አንድ አንድ አባቶች ደግሞ እንዚራ አኮርዲዮን ነው ይላሉ ። ለማንኛውም ቃሉ በመጽሐፍ ቅዱስ ተጠቅሷል ። “ሰብሕዎ በከበሮ ወበእንዚራ” መዝ 150 ።

ወአስተንፍሲ ውስተ አፉየ ከመ እኩን እንዚሁ ለበኩርኪ ። (አባ ጊዮርጊስ)

እለ ይነፍሑ እንዚራተ” (ፍትሐ ነገሥት 23 ቍ 8022)

ዛሬ ይህ ነው ተብሎ በቅርብ አግኝተን ባንጠቀምበትም እንዚራ አስደዳች የሆነ ድምፅ ያለው የመዝሙር መሣሪያ እንደ ሆነ እንማራለን እንገነዘባለን ።

10/ እምቢልታ፦ ታላቅ ዋሽንት ውስጡ ክፍት የሆነ የጥንት ዘመን ነገሥታት መኳንንት ደጃዝማች ብቻ ይጠቀሙበት የነበር ከቀርቅሐ ወይም ከሸንበቆ የሚሠራ ነው ። በብሉይ ኪዳን የታወቀ የመዝሙር መሣሪያ ነው ። መጽሐፍ ቅዱሳዊ መረጃዎች ። 1ዜና 15 ፥ 28 ። ኢዮ 21 ፥ 12 ፤ 30 ፥ 31 ። መዝ 150 ፥ 4 ።

አሁንም በሀገራችን በትልልቅ አድባራት ለምስጋና ሲውል ይታያል ። የከበረ የመዝሙር መሣሪያ ነው ። ከዋሽንት ጋር ተመሳሳይነት ስላለው ዋሽንትም በእንቢልታ ዓይን ስለሚታይ ሳይሆን አይቀርም መዝሙር የሚቀርብበት ።

11)  አርገኖን /ኦርጋን

በወርኃ ጥር በጥምቀት በዓል ላይ ብፁዕ አቡነ መልከ ጼዴቅ ስለ አርጋኖን  ተጠይቀው የሰጡትን መልስ መነሻ በማድረግ ማኅበረ ቅዱሳን ነኝ ብሎ ራሱን የሚጠራው የግለሰቦች ድርጅት ያሰማራቸውና ራሳቸውን መምህራን ብለው በሚጠሩ ግለሰቦች በኩል መልእክቱን አዲስ ትምህርት ወደ ቤተ ክርስቲያን ይግባ እንደ ተባለ አድርገው አባታችንን በመክሰስ ፣ በስደት የምትገኘውን የኢትዮጵያ ኦርቶ ዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን በመቃወም ምእመናንን ግራ ለማጋባት ጥረት አድርገዋል ። “የፈረንጅ መሣሪያ ወደ ቤተ ክርስቲያን በማስገባት አዲስ ሥርዓት እየሠሩ ስለ ሆኑ ተዋጉአቸው” ሲሉም ተሰምተዋል። «አዲስ ክርስቲያን ከጳጳስ ይቀናል» እንዲሉ ይህ ግብዝ ቡድን ራሳቸውን ለቤተ ክርስቲያን ሐዋርያዊ ተልእኮ አሳልፈው የሰጡትን ታላቅ አባት በማጣጣል እኔን ስሙኝ እነሱን ግን አትቀበሏቸው ሲል ማንነቱን ገልጧል ።

ይህ ቡድን ለቤ/ክ የማይታዘዝ የቤተ ክርስቲያንን መዋቅር አፍርሶ በራሱ መልክለመሥራት ሌትና ቀን በመሥራት ላይ ያለ ፤ የቤተ ክርስቲያንን ሀብተ ክህነት በማርከስየጀምላ ክህነት ፥ በገንዘብ በገዛቸው ሰዎች በኩል ለአባላቱ የሚያሰጥ፣ እንደ ስምዖንመሰርይ ጸጋ እግዚአብሔርን በገንዘብ ለመግዛት ጥረት በማድረግ ላይ የሚገኝ መሆኑንበሀር ቤት የሚገኙ አባቶች በመናገር ላይ መሆናቸው ዕለት ዕለት የምንሰማው የቤተክርስቲያን አሳዛኝ ክስተት ነው ። ማኅበሩ የቤተ ክርስቲያኒቱን ሕግና ሥርዐት በመፍረስ አባቶችንም በመደፋፈር ታሪክ ይቅር የማይለው በደል እየሰራ መሆኑን  ቤተ ክርስቲያን በመናገር ላይ ናት።[1]

ይህ ቡድን የቤተ ክርስቲያን ፈተና መሆኑ እየተገለጠ ባለበት በአሁኑ ወቅት የሕዝቡን ትኩረት ወደ ሌላ አቅጣጫ ለመለወጥ አስቦ እየዘራው ያለ የሀሰት መልእክት ነው ። ሁላችን ልናውቅ የሚገባው ነገር ቢኖር ብፁዕ አባታችን ያስተላለፉት መልእክት ፣ ከዚህ ቀደም በቅዱስ ሲኖዶስ ተወስኖ ውሳኔው የቤተ ክርስቲያኒቱ ልሳን በሆነው በነጸብራቅ መጽሔት በ2005 እ ኤ አቈጣጠር ታትሞ ለምእመናን የተዳረሰ ሲሆን ፤ አሁን እንዳዲስ ለም አነሣው?

በዚያውስ ላይ በሎሳንጀለስ ያሉ የኢትዮጵያ ኦርቶ ዶክስ ተዋሕዶ አብያተ ክርስቲያናት ላለፉት 30 ዓመታት በአርጋኖን እየተጠቀሙ እንዳሉ ያውቃል ፣ እንዴት አሁን እንደ አዲስ አድርጎ አባታችንን ለመክሰስ ተነሣ ? በስደት የሚገኙ አባቶች የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን በአርጋኖን እየዘመረች ሳለ፣ ይህ ቡድን ሳይፈጠር መሰደዳቸውን ያውቃል ፤ አርጋኖንን ከቤ/ክ አስወጥቻለሁና የእናንተም ሲኖዶስ ያጽድቅልኝ ብሎ አልጠየቀ። ለምን ከመሬት ተነሥቶ ይከሳል? ።

የአዲስ አበባው ሲኖዶስ በአርጋኖን ዘምሩ ብሎ ወስኗል በማለት በራሱ መጽሔት በሐመር ላይ የጻፈው ይህ ቡድን ፥ አርጋኖን የመዝሙር መሣሪያ መሆኑን ሳያውቅ ነውን ? [2] አሁን ለምን ሃይማኖቱን ካደ ? አሁን አሁን በነዚህ ሰዎች በኩል አርጋኖንን በተመለከተ ብዙ ነገር ሲባል እንሰማለን ።

ጥናቱም እነሆ !

አርጋኖን  እና  ስያሜው

አርጋኖን            በግእዝ

ኦርጋኖን            በግሪክ

አርቀኑን            በዓረብኛ

ዑጋብ   በዕብራይስጥ

ኦርጋን   በእንግሊዝኛ  [3]

ኦርጋኖን/church organ፦ የመዝሙር የማኅሌት የዘፈን የዜማ ዕቃ ነው ። አለቃ ኪዳነወልድ ክፍሌም ኦርጋንን ከነሥዕሉ በግእዝ መዝገበ ቃላታቸው ላይ አስቀምጠውታል።

አርጋኖን /ኦርጋን/ የተሠራው ለመጀመሪያ ጊዜ በአፍሪካ በናይል /በአባይ/ ወንዝ አጠገብ በእስክንድርያ በአንድ ግሪካዊ ዝርያ ባለው ሰው ነው ። የተሠራበት ዘመንም ከክርስቶስ ልደት በፊት (በብሉይ ኪዳን ዘመን) ሦስት ዓመት ቀድሞ ነው ። ስለዚህም ስለ ኦርጋኖን /ኦርጋን/ ታሪክ የተጠና ጥናት እንዲህ ይላል ። ኦርጋን /አርጋኖን/ ቀስ በቀስ እያደገ እየተቀናጀ ይምጣ እንጂ ከጥንት ጀምሮ ነበር ። በኋላ ግን ልዩ ልዩ ክፍል ያለው፦ “mouth organ, pipe organ, etc…” እየተባለ የሚጠራ እንዲሁም church organ የሚባለው ልዩ መሣሪያ ከጥንት ጀምሮ እንደ ነበረ ታሪክ ያሳያል ። “Greek engineer working in Alexandria in the third century BC….Which the organ was known in red, beginning in the Nile Delta region around Alexandria….’’[4]

ጥናቶች ሁሉ እንደሚያመለክቱት ኦርጋን /አርጋኖን/ ጥንታዊ የዜማ ዕቃ ነው ። በዘመናችን ያሉ አንድ አንድ ሰዎች በዘመናዊ መሣሪያ አንዘምርም ለማለት ከሚጠቅሷቸው ዋና ዋናዎቹ ምክንያቶች “ምዕራባዊ ነው” እና ‘ዘመናዊ ነው’ የሚሉ አስተሳሰቦች ሲሰነዝሩ ይሰማሉ ። በመሠረቱ በመቼም ይሠራ የትም ይሠራ አንድን ነገር ለመቀበል የሚከለክል  የቤ/ክ ቀኖና  የለም ።  ግን ታሪክ እንደሚያስረዳው ምዕራቡ ዓለም ለእድገቱ የሚጠቅሙትን ጥበቦችና ግኝቶች ከግሪክ እና ከአፍሪካ ለቃቅሞ ሲወስድ አብሮ የወሰደው መሣሪያ  ነው እንጂ ለመጀመሪያ ጊዜ የተሠራው አባይ ወንዝ አጠገብ ነው ።

ሮም በወደቀች ምሥራቅ ኤሮፕ ባደገች ጊዜ በቢዛንታይን ዘመነ መንግሥት እንዲሁም ቤተ ክርስቲያን ከመከፋፈልዋ በፊት በቈስጠንጢኖስ ዘመነ መንግሥት አርጋኖን /ኦርጋን/ ልዩ የእግዚአብሔር ስም መቀደሻ ፥ የዲያብሎስ ድል መንሻ ፥ የመዝሙር መምነሽነሽያ መሣሪያ እንደ ነበር ጥናቶች ያሳያሉ ። የእኛ አባቶች እነ ቅዱስ ያሬድ እነ አባ ጊዮርጊስም ስለ አርጋኖን /ኦርጋን/ ጣዕም ብዙ ዘምረው ጣዕሙን ተናግረው በመጻሕፍቶቻቸውም ጽፈው ምሳሌም መስለውበት እናገኛለን ። የቤተ ክርስቲያን ታሪክና መጽሐፈ ስንክሳርም ያመሰክራሉ።

የቅዱስ ያሬድ እና  የአባ ጊዮርጊስ ምስክርነት

  • ቅዱስ ያሬድ ስለ አርጋኖን /ኦርጋንምን አለ ?

የቤተ ክርስቲያን ሊቃውንት መልካም ነገርን ሁሉ በምሳሌ ይጠቀሙበታል ። አባታችን ቅዱስ ያሬድ ወንጌላዊ ዮሐንስ ወልደ ነጐድጓድን እያስታወሰ በዘመረበት ክፍል ፥ የቅዱስ ዮሐንስን አስተምህሮ ጣዕም የቃሉን መዓዛ ለመግለጽ ከተጠቀመባቸው አንዱ አርጋኖን /ኦርጋን/ ነው ። ለምሳሌ እመቤታችንን ቅዱስ ኤፍሬምና አባ ሕርያቆስ በመሰንቆ በጸናጽል በበትረ አሮን እየመሰሉ እንደ ተናገሩት ያለ ነው ።

ጥቅስ በግዕዝ ፥

  • ሰባኬ ወንጌል ዮሐንስ አርጋኖነ ትንቢት ዘይደምጽ ለቤተ ክርስቲያን ።

ትርጉም 

ሰባኬ ወንጌል ዮሐንስ ለቤተክርስቲያን መልካም ድምጽ የምትሰጥ ፥ በትምህርትህ የምትመስጥ የቤተ ክርስቲያን አርጋኖን /ኦርጋኖን/ ነህ” ። ይላል ቅዱስ ያሬድ ። [5]

ጥቅስ በግዕዝ

  • ከመ ዝብጠተ መሰንቆ አርጋኖን ስብሐቶሙ ለእሙንቱ ካህናት”

ትርጉም

የካህናቱ ምስጋና መሰንቆ አርጋኖን ሲመታ እንደሚመስጠው ድምጽ ነው” ይላል ቅዱስ ያሬድ ። [6]

ከዚህ በተጨማሪ ቅዱስ ያሬድ ለመጀመሪያ ጊዜ ዜማን ሲደርስ በተመስጦ ከሰማቸው የዜማ ድመሣሪያ ድምጾች አንዱ የአርጋኖን /የኦርጋን/ ድምጽ እንደ ነበር ገድለ  ቅዱስ ያሬድ ይናገራል ።

ጥቅስ በግእዝ፤

  • ወሰምዐ በህየ ቃለ እንዚራ ወቃለ አርጋኖን ወቃለ መሰናቅው እንዘ ይሴብሕዎ ወይዌድስዎ ወየአኵትዎ ለፈጣሬ ሰማያት ወምድር በስብሐት ወበማኅሌት በቅኔ ወበልዑል ዜማ ነግሀ ወሠርከ ይሴብሕዎ ለንጉሥ ዐቢይ በዓውደ መንበሩ ቅዱስ.።

ትርጉም በአማርኛ

በዚያም የእንዚራን ፥ የአርጋኖን ፥ የመሰንቆን ድምጽ እንዲሁም ሰማይንና ምድርን የፈጠረ ትልቁን ንጉሥ እግዚአብሔርን በስብሐትና በማሕሌት (በቅኔ) ከፍ ባለ ዜማ ጧትና በሰርክ በተቀደሰ ዙፋኑ ዙሪያ ሲያመሰግኑ ሰማ…” [7]

ከዚህ በላይ እንዳየነው አርጋኖን ከጥንት ጀምሮ በቤተ ክርስቲያን የነበረ አሁን ግን ስሙን እንጂ መልኩን ፣ ዜናውን እንጂ ግብሩን ባለማገናዘብ በአርጋኖን እንዘምራለን “በኦርጋን” አንዘምርም የሚሉ ሰዎች ተነስተዋል ። አነጋገራቸው በከበሮ እዘምራለሁ “በድራም” አልዘምርም ፤ ውኃ እጠጣለሁ “ዋተር” አልጠጣም እንደማለት ነው ። አርጋኖን ኦርጋን ነውና ።

  • አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ ስለ አርጋኖን /ኦርጋንየተናገሩት ምንድን ነው?

አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ ጥንት ለኮመልዝ ይባል በነበረው ዛሬ ወሎ ክፍለ ሀገር አማራ ሳይንት ልዩ ስሟ ሸግላ ከሚባል ቦታ ነው የተወለዱት ። አባታቸው ሕዝበ ጽዮን እናታቸው እምነ ጽዮን ይባሉ ነበር ። በትምህርት በገዳማዊ ሕይወት አድገው ብዙ መጻሕፍት ጽፈዋል ። ከመጻሕፍቶቻቸው መካከል “አርጋኖን” እና “እንዚራ ስብሐት” የሚባሉት ይገኙባቸዋል ። እነዚህ መጻሕፍት በመዝሙር መሣሪያዎች የተሰየሙ ናቸው። በአጠቃላይ አባ ጊዮርጊስ ከአሥር በላይ መጻሕፍት ደርሰው ተጋድሏቸውን ፈጽመው በ1413 ዓ.ም አርፈዋል ። አባ ጊዮርጊስ ከተነሡበት ዘመን ትንሽ ቀደም ብሎ በአስረኛው ምእተ ዓመት የኦርጋን አገልግሎት በቤተ ክርስቲያን በሰፊው ይሰጥበት የነበረበት ዘመን ነበር  የአርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ዲክሽነሪ  ስለ አርጋኖን በሰጠው ሐተታ ላይ ይናገራል ።[8]

አባ ጊዮርጊስም  የአርጋኖኑን ድምጽ እያስታወሱ ስለ እመቤታችን ምስጋና ሲያዘጋጁ በዘመናቸው በቅድስት ቤተ ክርስቲያን ጣዕም ያለው ውዳሴ ይቀርብበት በነበረው የመዝሙር መሣሪያ በአርጋኖን /በኦርጋን/ መስለው የምስጋናውን ጣዕም እንደ አርጋኖን  ድምጽ ለዛ ያለው እንዲሆን በማሰብ መጽሐፉቸውን አርጋኖን ብለውታል ። እመቤታችንንም በአርጋኖን /ኦርጋን/ መስለዋታል ። አርጋኖን የተሰኘውንም መጽሐፋቸውን መጻፍ ሲጀምሩ እንዲህ ይላሉ፥

ጥቅስ በግዕዝ

  • “ንጽሕፍ እንከ ዘንተ መጽሐፈ ዘይሰመይ አርጋኖነ ውዳሴ ወመሰንቆ መዝሙር ወእንዚራ…”

ትርጉም

“የምስጋና አርጋኖን የመዝሙር መሰንቆ እንዚራም የሚባል ይህንን መጽሐፍ መጻፍ እንጀምራለን….” ብለው መጽሐፉን ጀምረዋል ። አርጋኖን መሰንቆ እንዚራ የሚባሉት የማመስገኛ መሣሪያዎች ጣዕም ያለው ድምጽ እንደሚሰጡ አባ ጊዮርጊስ የደረሱት የጸሎት መጽሐፍ ነፍስን የሚያስደስት በመሆኑ መጽሐፉን አርጋኖን /ኦርጋን/ መሰንቆ እንዚራ በተባሉ መሣሪያዎች መስለው ተናግረዋል ። (አርጋኖን ዘሰኑይ ገጽ 9)  እንዲሁም ሊቁ ስለ አርጋኖን የሚከተለውን አብራርተዋል።

ጥቅስ በግዕዝ

  • “ወከማሁ ሊተኒ ርድአኒ ለወጢነ ጽሒፈ ውዳሴሃ ለመርዓተ አብ ወአሠልጥነኒ ካዕበ ለፈጽሞቱ ወለከናፍርየኒ ወአፉየ ረስዮን ከመ አርጋኖን ወኃይለ መንፈስ ቅዱስ ይዝብጦን ዘበልሳን ከመ ይንብባ ዘይኤድሞሙ ለሰማዕያን ወረስዮ ለአፉየ ከመ መሰንቆ ወድኅንጻ መንፈስ ይጉድኦ ከመ ይንቁ ሐዋዘ ወይሰንቁ ምዑዘ ። ወእለ ያጸምኡ ይኩኑ ፍሱሐነ በሰሚኦቱ ፥ ይትመሰጥ ህሊናሆሙ ላእለ ወአኮ ታህተ ፣ የሐልዩ ጽድቀ ወአኮ ኃጢአተ ፥ የሐልዩ ንጽሐ ወአኮ ርስሐተ ፥ የሐልዩ ይዋሄ ወአኮ ጽልሁተ ፥ የሐልዩ ትሕትና ወአኮ ትዕቢተ ፥ የሀልዩ ፍቅረ ወአኮ ቅንአተ ፥ የሐልዩ ልባዌ ወአኮ እበደ ፥ የሐልዩ ክብረ ወአኮ ኀሳረ ፥ የሀልዩ ዘኢይማስን ወአኮ ዘይማስን ፥ የሐልዩ ዘኢይበሊ ወአኮ ዘይበሊ ፥ የሐልዩ ዘበሰማያት ወአኮ ዘበምድር…” ።

ትርጉም ፤ “የአብ መሽራ የሆነችውን (የድንግልን) የምስጋና መጽሐፍ መጻፍ እንድችል እርዳኝ ። ለመፈጸምም እንድበቃ ሥልጣኑን ስጠኝ ። ከንፈሮቼን እና አንደበቴን በመንፈስ ቅዱስ ኃይል በልዩ ቋንቋ ሰሚዎችን ደስ የሚያሰኝ ነገር ይናገሩ ዘንድ እንደ አርጋኖን /ኦርጋን/ አድርግልኝ ። አንደበቴም እንደ መሰንቆ መልካም ሁኖ ይዘምር ዘንድ ምዑዝ ጣዕም ለዛ ያለው ድምጽ ይሰጥ ዘንድ ድኅንጻ መንፈስ /የመንፈስ ቅዱስ ቅኝት እንደ መሰንቆ አንደበቴን ያጫውተው ይምታው ። አርጋኖን /ኦርጋን/ መሰንቆ ሰሚዎቻቸውን ደስተኛ እንደሚያደርጉ እነርሱን የሰሙ በመሣሪያዎቹ ድምጽ እንደሚመሰጡ ፣ ይህንን የእመቤታችንን ውዳሴ የሚሰሙ ኅሊናቸው ይማረክ ። ኃጢአትን ያይደለ ጽድቅን ያስቡ ፥ ርስሐትን ያይደለ ንጽህናን ያስቡ ፥ ቅንአትን ያይደለ ፍቅርን ያስቡ ፥ ስንፍናን ያይደለ ጥበብን ያስቡ ፥ ውርደትን ያይደለ ክብርን ፥ የሚያልፈውን ያይደለ የማያልፈውን ፥ የሚያረጀውን ያይደለ የማያረጀውን ፥ በምድር ያለውን ያይደለ በሰማይ ያለውን ያስቡ….’  ማለት ነው ። [9]

አባ ጊዮርጊስ ከዚህ ሌላም መሰንቆ የሚሰነቃ መሣሪያ ለመሆኑ ፥ እንዚራ ደግሞ የድምጽ ፣ የእስትንፋስ መሣሪያ ስለ መሆኑ አርጋኖን /ኦርጋን/ ደግሞ በእጅ የሚነቃቃና የሚቃኝ የጣት መሣሪያ ለመሆኑ በልዩ ልዩ ስልት እሴብሕ ጸጋኪ በተባለው የዘወትር የቤተ ክርስቲያን ጸሎት ላይ ተናግረዋል ።  ለምሳሌ፦

ሀ) ስለ መሰንቆ እንዲህ አሉ ፥

ጥቅስ በግእዝ “ምንት ረባሑ ለመሰንቆ ለእመ አልቦ ዘይሰነቅዎ”

ትርጉም

“የሚሰነቃው ፥ የሚመታው ፥ የሚከረከረው ፥ የሚሞዝቀው ከሌለ የመሰንቆ ጥቅሙ ምንድን ነው” ይላል ። ለዚህም የተጠቀሙት የግእዝ ቃል “ሰንቀወ” ሰነቃ መሰንቆ መታ የሚለውን መሆኑን  ልብ ይሏል።

ለ) ስለ እንዚራ ደግሞ እንዲህ አሉ።

ጥቅስ በግእዝ “ወምንተ ይደምጽ ንቃወ እንዚራ ዘስቁል ለእመ ኢተነፍሐ በድርገታተ ማኅሌት” ይላል

ትርጉም

  • “የተሰቀለው እንዚራ በአንድነት ካልተነፋ የእንዚራ ድምጽ እንዴት ሊሰማ ይችላል?” ማለት ነው ።

ከዚህ ላይ እንዚራ የእስትንፋስ መሣሪያ ለመሆኑ አባ ጊዮርጊስ “ለእመ ኢተነፍሐ” ብለው ነፍሐ (ነፋ) በሚል ገላጭ አንቀጽ ስለ ገለጹት የሚነፋ ልዩ መሣሪያ መሆኑን ልብ ይሏል ። ድርገታተ ማኅሌት ማለት ደግሞ በዜና መዋዕል እንደ ተጻፈው ልዩ ልዩ የመዝሙር መሣሪያዎችን የሚጫወቱ ሰዎች በኅብረት በሚያቀርቡት የዜማ ድግስ ላይ እንዚራ የእስትንፋስ መሣሪያ ሁኖ የሚቀርብ የድግስ አካል መሆኑን ያመለክታል ።

ሐ)  ስለ አርጋኖን /ኦርጋን ደግሞ እንዲህ ብለዋል

ጥቅስ በግእዝ

  • “በነቀልቃለ ስብሐት ሑኪዮ ለአርጋኖነ ኅሊናየ ከመ ኢያርምም እም ስብሐታተ ፍቅርኪ” ይላል ።

ትርጉም “የፍቅርሽን ምስጋና ከማቅረብ አንደበቴ ዝም እንዳይል አርጋኖን /ኦርጋን/ ኅሊናዬን (ልቤን) በምስጋና ስሜት ንውጽውጽታ አንቀሳቅሽው/አነዋውጭው” ማለት ነው ።

“ነቀልቃል” የወጣበት “አንቀልቀለ” የሚለው የግእዝ ግሥና “ሑኪዮ” የሚለው አንቀጽ አርጋኖን /ኦርጋን በጣት እንቅስቃሴ ወይም ንውጽውጽታ መልካም ድምጽ የሚሰጥ መልካም የዜማ የመዝሙር መሣሪያ መሆኑን ስሙን ከነግብሩ ከነአፈጻጸሙ የሚገልጽ ነው ።

ከዚህ በላይ እንደተመለከትነው በጥንታዊት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የአርጋኖን /ኦርጋን/ አገልግሎት የነበረ ለመሆኑ ማስረጃ ነው ።  ዛሬም ቤተ ክርስቲያን የመዝሙር መሣሪያዎችን ስትቈጥር አርጋኖን ብላ በቋንቋዋ ኦርጋንን አብራ በውሳኔዋ ውስጥ ጠቅሳዋለች ። [10]

  • የቤተ ክርስቲያን ታሪክ ምስክርነት

የዓለም ቤተ ክርስቲያን ታሪክ እንደ ሚነግረን፣ ቤተ ክርስቲያን ካቶሊክ ኦርቶዶክስ ተብላ ከመለያየቷ በፊት በሠለስቱ ምዕት ዘመን አርጋኖን ወይም “ቸርች ኦርጋን” የሚባለው የቤተ ክርስቲያን አይነተኛ የመዝሙር መሣሪ እንደ ነበር ይናገራል ።[11]   “ወሪድየ ብሄረ ሮሜ ለቤተ ክርስቲያን ርኢክዋ = ሮም ወርጄ ቤተ ክርስቲያንን አየኋት” ሲል የዘመረው ቅዱስ ያሬድ ስለ አርጋኖን ጣዕም በድርሰቱ መስክሯል ።

  • የመጽሐፈ ስንክሳር ምስክርነት

በዘመነ ሰማዕታትም አርጋኖን የታወቀ የመዝሙር መንፈሳዊ መሣሪያ ነበር ። ስለዚህም «ወበህየ ሰምዑ አርጋኖነ ወብዕዛ ወይቤሉ ምንትኑ ዘንሰምዕ» «በዚያም የአርጋኖንና የብዕዛ ድምጽ ሰሙ ፤ የምንሰማው ምንድነው አሉ» በማለት እንደ ተናገሩ በመጽሐፈ ስንክሳር ተጽፎአል ። [12]

ኢትዮጵያ ሀገራችን የዛሬን አያርገውና ከነአውሮፓ በፊት የሠለጠነች ፥ ግሪክን ግብጽን በሥልጣኔ የምትመስል ሀገር ስለ ነበረች የአርጋኖን /ኦርጋን/ አገልግሎት በኢትዮጵያ የታወቀ እንደ ነበር የሚያጠራጠር አይደለም ። የተፈጠረው እራሱ አባይ ዳር ነውና ። ግን ደሃን ሲያጣ ማንም አይወደውምና ታሪኩን ሁሉ ባዕዳን ስለወሰዱት እንኳን አርጋኖን መሰንቆው ሁሉ ከዕቃ ቤት ስለ ተባረረ እኛም የኛ ሳይመስለን ፥ ምእራባውያንም የኛ ነው ለማለት ሲከጅሉ ይታያል ። ግን ምሁራን አልተቀበሏቸውም ። በጥናታቸውም አፍሪካዊ የአባይ ዳር ግኝት የዜማ ዕቃ እንደ ሆነ ጽፈዋል ።

በዚህ ድርጅት (ማቅ) ውስጥ የሚገኙ አንድ አንድ ዓይነ ልቡናቸው የተያዘባቸው ሰዎች ተነሥተው ቤተ ክርስቲያንን ግራ ለማጋባትና የያዘችውን ለማስጣል ደፋ ቀና ማለት ከመጀመራቸው ቀደም ሲልም አርጋኖን /ኦርጋን በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ልዩ የምስጋና የቅዳሴ የውዳሴ መሣሪያ ሁኖ በታላላቅ አድባራት እግዚአብሔር ሲመለክበት ቆይቷል ።

ዛሬ ዛሬ ግን ቤተ ክርስቲያንን የምስጋና መሣሪያዋን እኛ እናውቅልሻለን ፤ በዓለም የምንዘፍንበት ይህ ስለ ሆነ ይህንን ለዘፈን ተዪልን ፤ ዝም ብለሽ ተቀመጭ ብለው ባላዋቂ አንደበታቸው ቤተ ክርስቲያንን በማውገዝ አርጋኖን እንዳይዘመርበት ሲያከላክሉ በአርጋኖን /ኦርጋን/ መዘመር እንደ አንቀጸ ሃይማኖት ታይቶ ሊቃውንቱ በጨዋዎቹ ፤ ጳጳሳቱ በነጋዴዎቹ ሲወገዙ መስማት እየተለመደ መጥቷል ።

በመሠረቱ በኦርጋን መዘመር በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ፣ በግብጽ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ፣ በአርመን ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ፣ በሶርያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን እና በህንድ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን እንዲሁም በአለም በሚትገኝ የክርስቶስ ቤተ ክርስቲያን የተለመደ የነበረ ያለ ነው ። አሁን አሁን ግን የኛዎቹ ቢጽ ሐሳውያን ቤተ ክርስቲያን ከአፄ ኃይለ ሥላሴ ዘመነ መንግሥት ጀምሮ እንኳ ለ40 ዓመታት ያህል በቅድስት ሥላሴ ካቴድራል፣በግቢ ገብርኤል፣ በልደታ ለማርያም፣ በዮሐንስ ወልደ ነጎድጓድ  እግዚአብሔርን ስታመልክበት ከኖረች በኋላ ማኅበርተኞች ለግላቸው በግላቸው ለቢዝነስ ያቋቋሙትን ማኅበር ይጻረርብናል ብለው የገመቱትን እና እንደ ጐባን ያዩትን ሃይማኖተ አበውን እና የቅድስት ሥላሴን ሰንበት ትምህርት ቤት ለማጥፋት ከተጠቀሙባቸው መንገዶች እንደ አንድ አማራጭ አድርገው የወሰዱት በኦርጋንን ይዘምራሉና መናፍቃን ናቸው ብሎ መክሰስን ነበር ። ይህ ራሱን የቻለ ታሪክና  ምክንያት ያለው በመሆኑ ወደፊት እንመለከተዋለን።

  • የጥንት መጽሐፍ ቅዱስ ተርጓሚዎች ምስክርነት

ልዩ ጥቅስ

ግእዝ ፥ “ሰብሕዎ በከበሮ ወበትፍሥሕት

ሰብሕዎ በአውታር ወበእንዚራ”

አማርኛ ፥ በከበሮና በዘፈን አመስግኑት

በአውታርና በእምቢልታ አመስግኑት…። መዝ 150 ፥ 4 ።

English

“Praise Him with tumbrel and dance praise Him with stringed instruments and organs” ። Psalm 150:4 …King James Version

በዚህ ትርጉም ላይ የምንማረው ነገር ኦርጋን የመዝሙር መሣሪያ መሆኑን ነው ። ነገር ግን ሁላችን እንደምናውቀው ብዙ አይነት መሳሪወችን የያዘ  የዜማ መሳሪያዎች ምዕላድ በመሆኑ ከዚህ ላይ በውስጡ ካሉት መሳሪዎች ንዱን በግእዝ እንዚራ በአማርኛ እንቢልታ የተባለውን መሳሪያ ነው አርጋን ያለው። ያ ማለት ግን አርጋኖን ማለት እንዚራን ብቻ ነው የሚወክለው  ማለት አይደለም። እንዚራንም ስለሚያጠቃልል ነው እንጅ ።  [13]  ይህም ታሪካዊ የትርጉም ስራ አራጋኖን በቤተ ክርስቲያን ታሪክ ያለውን ቦታ ያሳያል።

  • በአርጋኖን ላለመዘመር የፈለጉ ሰዎች የሚያቀርቧቸው ምክንያቶችና መልሶቻቸው
  1. «አርጋኖን የመጽሐፍ ስም ነው እን የመዝሙር መሣሪያ አይደለም» ይላ

ይህ አባባላቸው ግን ቀድመው በመጽሔታቸው ከጻፉት ጋር ከመጋጨቱም በላይ ካለማወቅ ወይንም ኅሊናን በመሸንገል የተሰነዘረ ሐሳብ ነው ። ከጥንት ጀምሮ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አባቶች ዘንድ የታወቀና የተወደደ የመዝሙር መሣሪያ እንደ ሆነ በቅዱስ ያሬድ ድርሰት ፣ በአባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ ድርሰት ፣ በመጽሐፈ ስንክሳር ተጠቅሶ እንደሚገኝ በዚህ ጥናታዊ ጽሑፍ ውስጥ እናሳያለን ።

ሌላው የማኅበሩ ተናጋሪ ደግሞ አርጋኖን ድምጽ እንጂ የመዝሙር መሣሪያ አይደለም ይላል ። [14] አርጋኖን ድምጽ እንጂ መሣሪያ አይደለም የሚል የቤተ ክርስቲያን መጽሐፍ የለም ። ለምን እንደ ሰናዖር ሰዎች ቋንቋቸው ተደበለቀ ?

ሌላው ሰባኪያቸው ደግሞ አርጋኖን ወይም ኦርጋን ንዋየ ማኅሌትን የሚወክል ስያሜ በመሆኑ በኪንግ ጀምስ ትርጉም መጽሐፍ ቅዱስ ላይ ተጠቅሷል ይላል ። ይህም ከላይ ከጠቀስነው ተናገሪ ይለያል ። [15]

በድፍረት ኃጢአት ወድቀው ሌላውን ከሚበክሉ እርገጠኞች ባልሆኑበት ነገር ላይ ተነሥተው ሕዝበ ክርስቲያንን ከማሳሳት ይልቅ የቤተ ክርስቲያን አባቶችን ቢጠይቁ አይሻልም ነበርን ? ። ነገር ግን ጥንታውያን የብራና መጻሕፍቶቻችን የሚመሰክሩት አርጋኖን የሚጣፍጥ ድምጽ የሚሰጥ የመዝሙር መሣሪያ መሆኑን ነው ። ነገር ግን ስለ አርጋኖን የሚናገሩት ሰዎች የግእዝን ቋንቋ ባለመረዳታቸው ምክንያት የተሳሳተ መረጃ በመስጠት ሕዝቡን ግራ ያጋባሉ ።

ከዚህ የሚከተለውን ጥናታዊ ጽሑፍ  ስለ አርጋኖን ማቅረብ ያስፈለገበት ምክንያት ፣ ቤተ ክርስቲያን አርጋኖንን የመዝሙር መሣሪያ የምትለው ከጥንት ጀምሮ ሀብቷ ስለ መሆኑም ከቤተ ክርስስቲያን መጻሕፍት ፣ ከቤተ ክርስቲያን ታሪክ ፣ ከመዛግብተ ቃላት የተገኘውን መረጃ ለምእመናን ግልጽ ለማድረግ ነው ።

የፈለገ ያለመሣሪያ ሊዘምር ይችላል ። በመሣሪያ ሊዘምር የሚፈልግን ደግሞ እኔ እቃወማለሁና አትዘምር ማለት ተገቢ አይደለም ። “የሚበላው የማይበላውን አይንቀፈው” እንዳለ ቅዱስ ጳውሎስ አንዱ ሌላውን ሳይነቅፍ በፍቅር መኖር ሲቻል ፣ በአርጋኖን የሚዘምሩ አብያተ ክርስቲያናትን መኮነን ትልቅ ስሕተት መሆኑን ለማሳየት ነው

  1. በኦርጋን ዳዊት አልዘመረም  ሁሉ ተገልጾለት ትንቢት ሲናገር ወደፊት ኦርጋን እንደሚሠራተገልጾለት ትንቢት አልተናገረም” ይላሉ ።

እንደነዚህ ሰዎች ሃሳብ በዳዊት ዘመን ባልነበረ መሣሪያ ወይም ዳዊት እንደ ምሥጢረ ሥጋዌው ሁሉ ትንቢት ባልተናገረበት መሣሪያ መዘመር መጠቀም ስሕተት ነው ። በመሠረቱ ነቢያት ኃላፍያት (ያለፉትን) መጻእያት (የሚመጡትን) ሁኔታዎች ተገልጸውላቸው መናገራቸው እውነት ነው ። ግን ሃብተ ትንቢታቸው የተመሠረተው መንፈሳዊ ነገር በሚከናወንባቻው መሣሪያዎች ላይ ሳይሆን በምሥጢረ ሥጋዌ በክርስቶስ ቀዳማዊ እና ዳግማዊ ምጽአቶች ላይ በአጠቃላይ በብሉያትና በሐዲሳት በተጠቀሱት ተስፋዎች ላይ የተመሠረተ ነው ።

ይህንን ዓይነት ነገር የሚናገሩ ሰዎች በስልክ እንደሚያወሩ ፣ በመኪና እንደሚሄዱ ፣ በኢንተርኔት እንደሚገናኙ ፣ በአውሮፕላን ፣ እንበሚበሩ ዳዊት ትንቢት ስላልተናገረ እነዚህን ነገሮች መጠቀም የለባቸውም ማለትነው ። በእርግጥ እነሱ ቤተ ክርስቲያንን ከምእመናን መንፈሳዊ ሕይወት ለይተው ስለሚመለከቷት የእነርሱ ክርስትና ሕይወት ቤተ ክርስቲያን ቅጽር ውስጥ ስለ ሆነ ነጠላውም መንፋሳዊ መስሎ መታየቱ ከዚያው ከቤተ ክርስቲያን በቻ በመሆኑ ውጪ እንዘፍንበታለን ቤተ ክርስቲያን ውስጥ እናመልክበታለን እንደሚሉ ጥርጥር የለውም ።

ሌላው ቅዱስ ያሬድ በመቋሚያ የዘመረው ዳዊት ስለ መቋሚያ ትንቢት ተናግሮ አይደለም እግዚአብሔር ገልጾለት ነው እንጂ ። አንድ አንድ ጊዜ ደግሞ በመጽሐፍ ቅዱስ ስለ ኦርጋን አልተጻፈም ይላሉ ። ስለ መቋሚያስ የት ተጽፏል በዋሽንት ዘምሩ የሚልስ የት ይገኛል ? መጽሐፍ ቅዱስ በሕይወት መልእክት ላይ የተመሠረተ መጽሐፍ ነው ። እግዚአብሔር ወደ ፊት አዲስ ነገር በሰው ሕይወት ስለማይሠራ እንዳትጠቀሙ አላለም ። መጽሐፍ ቅዱስ በአርጋኖን አትዘምሩም አላለም ። የቤተ ክርስቲያን ሥርዓትም በአርጋኖን /ኦርጋን/ እንዳይዘመር አይከለክልም ። አትዘምሩ የሚል ሳይሆን ዘምሩ የሚል ሥርዓት ነው ቤተ ክርስቲያን ያላት ። ከጥንት ጀምሮ ኦርጋን የቤተ ክርስቲያን መሣሪያ ነውና ።

  1. የዘፈን መሣሪያ ስለ ሆነ አንዘምርበትም” ይላሉ ።

ምነው ታዲያ መለከት በገና ክራር ለዘፈን በዘፋኞች የተሠሩ ለሥጋ ፈቃድ የተቀጠቀጡ የዘፈን ዕቃዎች የጣዖት ማጀቢያዎች አልነበሩምን ? በመሠረቱ ችግሩ ከዕቃዎቹ ላይ ሳይሆን ከተጠቃሚዎቹ እና ከአጠቃቀማቸው ላይ ነው ። እግዚአብሔር ለምስጋና እንጂ ለዘፈን ስላልፈጠረን በኦርጋን ልንዘምርበት እንጂ ልንዘፍንበት አይገባም ። ቤተ ክርስቲያንም ለዘፈን እውቅና አትሰጥም ። እነ ከበሮም እነ መሰንቆም እኮ ጠጅ ቤት ስለ ገቡ አንዘምርባቸውም ልንል ነው ?

  1. ባህላችን አይደለም የምዕራባውያን መሣሪያ ነው” ይላሉ

በመሠረቱ ኦርጋን /አርጋኖን/ አፍሪካዊ ግኝት የቤተ ክርስቲያን ሃብት ቀደም ሲል እንደተመለከትነው እነ ቅዱስ ያሬድ ጣዕሙን ያደነቁት ፤ እነ አባ ጊዮርጊስ የተመሰጡበት ፤ በኢትዮጵያ ጥንታዊ የሥልጣኔ ዘመን የማኅሌት ሀብት ንብረት ሁኖ የነበረ ፤ እነ መሰንቆ እነ በገና እነ መለከት ከዕቃ ቤት ሲሰደዱ አብሮ ወጥቶ የቀረ ፥ ስሙ በዜማና በጸሎት መጻሕፍት እየታወሰ የሚገኝ ጥንታዊ የቤተ ክርስቲያን ሀብት እንደ ሆነ የቤተ ክርስቲያን መጻሕፍት ምስክሮች ናቸው ።

በመሆኑም ምዕራባውያን ክእስክንድርያ  ወሰዱት እንጂ እኛ ከእነርሱ አላመጣነውም። ግን እነሱ ከአፍሪካ ወስደው አሳድገው ንብረታቸው አስመሰሉት ። በጥቁር ሕዝብ ላይ ነጮች የፈጸሙትን ግፍ ያየ ያነበበ ወጣት ሀብቱን በባሪያ ፈንጋዮች ዓይን በመመልከት ፈራው ። «እባብ ያየ በልጥ በረየ» እንዲሉ ። ያ ግን ያላደገ አስተሳሰብ ውጤት እንጂ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ጥንታዊ ታሪክና  ሥርዓት የኦርጋንንም የመዝሙር መሣሪያነት የሚያጠፋ አይደለም ። ለዚህም ከዚህ በፊት ያነበብነው መረጃ በቂ ነው ።

  1. ከበሮን ጸናጽልን እና መቋሚያን ከቤተ ክርስቲያን ለማጥፋት ነው” ይላሉ

የሚያሳዝነው ሰው ስላማያውቀው ነገር ሲናገር መሰማቱ ነው ። ለመሆኑ ማነው ስለዚህ ነገር ሊያስብ የሚገባው ? በእርግጥ ማንም እንደ ክርስቲያንነቱ ማሰብ የሚገባውን ማሰብ ይችላል ። ግን ከላይ የተጠቀሱትን የመዝሙር መሣሪያዎች ድርሻ የሚወስድ አይደለም ። ለሁሉም ጊዜ የአጠቃቀም ስልት መፍጠር ስለሚቻል እና ስለ ተቻለ የመሰንቆ መኖር ከበሮን እንደማያጠፋ የኦርጋንም መኖር ሌሎቹን መሣሪያዎች አያጠፋም ።

በተለያዩ ጊዜያት ወደ ቤተ እግዚአብሔር የገቡ ንዋየ ቅድሳት የየራሳቸው ድርሻ እና ጥቅም አላቸው። አንዳቸው ያንዳቸው መተኪያ እንዲሆኑ የተመሪጡ አይደሉም ። እነዚህን ንዋየ ቅድሳት ሁሉንም ለተዘጋጁበት አገልግሎት ለተመረጡበት ሥራ ስንጠቀምባቸው በቤተ ክርስቲያን አገልግሎት ውስጥ የየበኩላቸውን አስተዋጽኦ ያደርጋሉ ። ለምሳሌ ዛሬ በመሰንቆ መዝሙርን ስናጅብ መሰንቆው የጸናጽልን ወይም የከበሮን ቦታ እንዲወስድ የተመረጠ ዕቃ ሁኖ አይደለም ። ሁኖም ግን ምክንያቱ በቤተ ክርስቲያን አገልግሎት ለመሰንቆ የራሱ ድርሻ ስላለው ለዚያ ተፈልጐ ነው ። እንደዚሁም ኦርጋንም /አርጋኖንም/ ከበሮንና ጸናጽልን እንዲያስቀር ወይም እንዲተካ የታሰበ ሳይሆን የተሠራበትን የራሱን ጥቅም እንዲሰጥ ለማድረግ ነው እንጂ ። ቤተ ክርስቲያን በብሉይ ኪዳን መጽሐፈ ዜና መዋዕል ካልዕ 5 ፥ 11-14 እንደ ተጠቀሰው በጸናጽል ፥ በመሰንቆ ፥ በበገና ፥ በዜማም ዕቃ ሁሉ የሠለጠነ የመዘምራን አካል ኖሯት እነዚህን ሁሉ አስማምታ የእግዚአብሔርን ስም እንድትቀድስበት ልዩ ልዩ የመዝሙር መሣሪያዎችን ያዘች እንጂ አንዱን በአንዱ ለማጥፋት አይደለም ።

  1. የባሕር ማዶ መሣሪያ ነው” ይላሉ

መልሱ አይደለም ነው ። አለመሆኑን ከዚህ ቀደም አይተናል ። ቢሆንስ በሃይማኖት የተቀበልናቸው ነገሮችን ከአካባቢ እና ከቀለም ጋር ማዛመድ የዘመናችን ፖለቲካ ነው እንጂ ክርስቲያናዊ ነገር አይደለም ። ቤተ ክርስቲያንም ዓለም አቀፋዊ (እንተ ላዕለ ኲሉ)ናት ። መጽሐፍ ቅዱስ በጥቁሮች ስላልተጻፈ አንቀበልም ልንል ነውን ? ይህ ዓይነቱ መንፈስ ከእግዚአንብሔር አይደለም ።

  1. ቅርሳችንን ለመጠበቅ ነው” ይላሉ

ቤተ ክርስቲያናችን ለሰዎች መዳን ለክርስቲያኖች እውነተኛ ሕይወት እድገት ያዋለቻቸው ነገሮች ከጊዜ በኋላ በሚያምኑትም በማያምኑትም ሕዝቦች ዘንድ የባህል መግለጫዎች መሆናቸው እውነት ነው ። ቤተ ክርስቲያን ጥንታዊ ከሆኑ ሀብቶችዋ አንዱ አርጋኖን እንደ ሆነ በሚገባ ተመልክተናል ። ስለዚህ በአርጋኖን መዘመር ሀብትን መጠቀም እንጂ ወደ ቤተ ክርስቲያን አጥፊ ነገርን ማስገባት አይደለም ። አንድ አንድ ጊዜ ደግሞ ዘመናዊ መሣሪያ ስለ ሆነ አንጠቀምም ይላሉ ። ጥንታዊነቱ አጠያያቂ ባይሆንም በዘመናዊ መሣሪያ መጠቀምም ስህተት አይደለም ።

ቤተ ክርስቲያን ያላትን ጠብቃ እንዲሁም ምእመናን ሕይወታቸው በምስጋና የሚሞላበት ፤ አእምሮአቸው በመዝሙር የሚደሰትበት ፤ የእግዚአብሔርን ክብር የሚገልጹበት ለበጐ የሚውል ነገርን በየጊዜው እግዚአብሔር ለሰዎች ከሰጠ ትጠቀምበታለች ። የኤሌክትሪክን መብራት መጠቀም ፣ ስልክን ፣ ሬዲዮን ፣ ልዩ ልዩ የኢንፎርሜሽን መሣሪያዎችን ዓለም ለፖለቲካዋ እና ለሥጋዊ እርባና ስትጠቀም ቤተ ክርስቲያን ደግሞ ለበጐ ትጠቀምበታለች ። ወንጌል ታስተምርበታለች ። እንደዚሁ ሁሉ የመዝሙር መሣሪያም ለእግዚአብሔር ክብር ቢውል ምናልባት ሜልኮል በመቃብር ውስጥ የወለደቻቸው ፥ የመዝሙር ጠላቶች ፥ ዘማርያንን ዘፋኝ ባዮች ፥ የዳዊት ተቃዋሚዎች ካልሆኑ በቀር ምንም የሚከለክል መጽሐፍ በቤተ ክርስቲያናችን የለም ። ዘምሩ የሚል ግን ሞልቷል ።

በመሠረቱ ሕይወት የሚድንበት ከሆነ ፥ የክርስቶስ ወንጌል የሚገለጥበት ፥ ዘፋኝ ተለውጦ ዘማሪ የሚሆንበት መሳሪያ ፥ እንዲሁም ጥንታዊ የዜማ ዕቃ ሲሆን ፥ በኦርጋን ላይ ለምን ያላዋቂ አውጋዦች እንደ ተነሡ ግልጽ አይደለም ። ቅዱስ ዳዊት ግን ባለን ነገር ፣ ኃይል ፣ ጥበብ ሁሉ እግዚአብሔርን እንድናመልክ ፈቅዷል ። በዘመኑ የነበሩትን የዘፈን ዕቃዎች ዘምሮባቸዋል ። በአዲስ ቅኔ ፣ ድምጽ ባለው የመዝሙር ዕቃ ሁሉ እግዚአብሔርን እንድናመልክ ተናግሯል ። መዝሙር 150ን በሙሉ ያንብቡ ። በዳዊት ዘመን ቢገኝ ዳዊት የእግዚአብሔር ሰው ስለ ሆነ ይዘምርበት ነበር እንጂ ዝፈኑበት አትዘምሩበት አይልም ነበር ።

  1. የቤተ ክርስቲያን ሥርዓት አይደለም” ይላሉ ።

በአርጋኖን /ኦርጋን/ መዘመር የቤተ ክርስቲያን ሥርዓት አይደለም ብሎ ቅዱስ ሲኖዶስ የወሰነበት ጊዜ እና ዘመን የለም ። በአንጻሩም በአርጋኖን እንድንዘምር ቅዱስ ሲኖዶስ ያልወሰነበት ጊዜ የለም ። ቤተ ክርስቲያን የዜማ ዕቃዎችዋን ስትቈጥር ከአባቶችዋ እንዳገኘችው አርጋኖንን ከተራ ቍጥር ያወጣችበት ጊዜ የለም ። ለዚህም የነሱ ሐመር መጽሔት ሳትቀር ምስክር መሆኗን አይተናል። አርጋኖን ኦርጋን መሆኑን ማስተዋል ደግሞ የእኛ ድርሻ ነው ። ይኸውም ሊታወቅ በአዲስ አበባ ያሉ አባቶችም ሆነ በአሜሪካ ያሉ አባቶች በአርጋኖን እንዲዘመር ፈቅደዋል ። በየውሳኔዎቻቸው ዝርዝር ላይ ይህንን ሳይጠቅሱ ያለፉበት ጊዜ የለም ። ችግሩ የቋንቋ እንጂ የምሥጢር አይደለም ።

በመሠረቱ የአርጋኖን /ኦርጋን/ ታሪካዊ አመጣጥ ጥንታዊና በመንፈሳዊው ዓለምም ትልቅ መንፈሳዊ መሣሪያ መሆኑን ተመልክተናል ። በጥንታዊቷ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንም እንደ ሌሎች አኀትአብያተ ክርስቲያናት ሁሉ ከጥንት ጀምሮ የአርጋኖን /ኦርጋን/ አገልግሎት የነበረና ያለ መሆኑን ከእነ ቅዱስ ያሬድ ፥ ከእነ አባ ጊዮርጊስ ድርሰቶች ፥ ከቤተ ክርስቲያን ታሪክ ፥ ከጥናት ጽሑፎች ፥ ከልዩ ልዩ መዝገበ ቃላት ተረድተናል ። በእኛ ቤተ ክርስቲያን የአርጋኖን አገልግሎት እንደ ከበሮው ፥ እንደ መቋሚያው ፥ እንደ ጸናጽል እስከ አሁን በቅርቡ በቤተ ክርስቲያን ሲዘመርበት በሰፊው አላየንም ማለት ከሆነ ጥያቄያቸው ፥ ቤተ ክርስቲያን ካሳለፈቻቸው ፈተናዎች ሊያጠፏት ተነሥተውባት ከነበሩ ጠላቶቿ ከነዮዲት ጉዲት ፥ ከእና ግራኝ አህመድ  ፥ ከነ ድርቡሽ ፥ ወዘተ   የተነሣ ብዙ የጥበብ የበረከት መጻሕፍቶችዋ ጠፍተዋል ። አርጋኖን ብቻ ሳይሆን የመዝሙር መሣሪያዎቿ ሁሉ ተቃጥለዋል ። እንደ መሰንቆ ፥ እንደ በገና ፥ ዋሽንት ፥ እንደ እንዚራ ያሉት ሁሉ ከቤተ ክርስቲያን ዕቃ ቤት ተሰደው ቀርተዋል።

እንዚራ እና አርጋኖን ደግሞ በመጻሕፍት ብቻ ስማቸው እየታወሰ ቤተ ክርስቲያንም የመዝሙር መሣሪያዎችዋ እንደ ሆኑ እያስተማረች መልካቸውንና ስማቸውን ለማዛመድ እስክትቸገር ድረስ ከቤተ ክርስቲያን እርቀው ቆይተዋል ። ይህም አያስገርምም ። ዛሬ እነዚህ የዜማ ዕቃዎች ብቻ ሳይሆኑ በመሰንቆ በእንዚራ በበገና መዘመርም በመጽሐፍ እንጂ በግብር በማኅሌት አገልግሎት ሲሰጥ አይታይም ። ግን መጻሕፍቱ ሁሉ ይመሰክሩላቸዋል ። ይልቁንም መሰንቆ ከዕቃ ቤት ወጥቶ የአዝማሪ  መሣሪያ ሁኖ ሲኖር ዛሬ አልፎ አልፎ በአንዳንድ ዘማሪዎች በኩል በቤተ ክርስቲያን አገልግሎት እየሰጠ ይታያል ። ነገም ሌሎቹ እንዲሁ ሊመለሱ ይገባል ። በክፉ ዘመን ያጡትን ንብረት እንደ ጠፋ ይቅር ማለት ተገቢ አይደለምና ። ለምሳሌ ፥ እንኳንስ ይሄን ነባሩን ነገር ለቤተ ክርስቲያን የሚጠቅም ከሆነ ሁሉን ማድረግ ይገባል ።

ቀድሞ ወንጌል እንደ አሁኑ ማታ ማታ ሥራዬ ተብሎ አይሰበክም ነበር ። አሁን ግን ያ ሁኗል ። ባህላችን አይደለም አንልም ። ቀድሞ የወጣት ሰንበት ትምህርት ቤት አገልግሎት አልነበረም ። ዛሬ ግን አለ። ባህላችን አይደለም አንልም ። ጠቃሚ ነውና ። የአርጋኖን አገልግሎት ግን ከዚህ ሁሉ በተለየ መንገድ የነበረ ፥ ግን በችግር ዘመን የቀረ ነው እንጂ አዲስ ነገር አይደለም ። ይኸውም ሊታወቅ ለኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ወርቃማው ዘመን በሚባለው በአፄ ኃይለ ሥላሴ ዘመነ መንግሥት ከ1940ዎቹ ጀምሮ ከዚም በኋላ እስከ 1988 ዓም ድረስ በቤተ ክርስቲያን ሲዘመርበት ቆይቷል ። አኮርዲዮን እንዚራ ነው ብለው አበው ስለ ተቀበሉት በአክሱም ጽዮን ፥ በተድባበ ማርያም ፥ በቆማ ፋሲለደስ ፥ በደብረ ብርሃን ሥላሴ ጐንደር ፥ በማኅደረ ማርያም ደብረታቦር መድኃኔዓለም ፥ እንደ ነበረ አባቶቻችን የዓይን ምስክሮች ናቸው። ይህንን ሁሉ ያተትኩት በኦርጋን መዘመር ጥንታዊ ሥርዓታችን ነው ፣ ከዚያም አልፎ ተርፎ   ለቅዱስ ያሬድ ዜማ በጣም ተስማሚ ፥ ለሊቃውንቱ ለዛና ጉሮሮ የዜማ ስልት የሚስማማ አብሮ የሚሄድና የሚንቆረቆር በመሆኑ ፣ ከማንም የበለጠ የቅዱስ ያሬድ የዜማ ሀብት ላላት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክትስቲያን ፥ በጣም የሚጠቅም ልዩ ሀብት ነውና የሚጠቀሙበትን መቃወም አይገባም ለማለት ነው ።

  1. አርጋኖን ርጋን አይደለም ይላሉ ?

ስሕተት ነው- የግእዝ መዝገበ ቃላት በግልጥ አርጋኖን ምን ማለት መሆኑን በሥዕል ሳይቀር አስቀምጦታል ። በግእዝ መዝገበ ቃላት ስሙ ከነትርጉሙ ሥዕሉ ሳይቀር ተሥሎ እናነባለን ። ይህንንም በዝርዝር ተመልክተናል ። ከዚህም በተጨማሪ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫም ሰዎች በጣታቸው የሚጫውቱበት መሣሪያ መሆኑን አመልካች በሆኑ የግእዝ አናቅጽ ገልጦታል ።

  1. አርጋኖንን የቀድሞው ሊቀ ሥልጣናት በኃይል ወደ ቤተ ክርስቲያን አስገቡት በኋላ ግን ቅዱስ ሲኖዶስ ከቤተ ክርስቲያን አስወጣው ይላሉ?

አርጋኖን ወደ ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል የገባው በእርግጥ በአፄ ኃይለ ሥላሴ ዘመን መሆኑ እውነት ነው ። ነገር ግን ቅዱስ ሲኖዶስ ሳያውቅ ሳይሆን ቅዱስ ሲኖዶስ ፈቅዶ ከብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ባስልዮስ እስከ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ በቤተ ክርስቲያን ሰፊ አገልግሎት ሲሰጥበት እንደ ነበር ብዙዎቻችን እናውቃለን ።

አቡነ ጳውሎስም ከተሾሙ በኋላ የመጀመሪያወቹን ኤጲስቆጶሳት ሲሾሙ ቅዳሴው በአርጋኖን ታጅቦ እንደ ነበር ይህ ጸሐፊ የዓይን ምስክር ነው ። በኢትዮጵያ ኦ/ተ/ቤ/ክ ታሪክ የመጀመሪያ የሆኑት የአማርኛ መዝሙራት በያሬዳውያን ሊቃውንት ተዘጋጅተው ከኖታው ጋር በመጽሐፍ መልክ በሊቃውንት ጉባኤ ተመርምሮ በቅዱስ ሲኖዶስ ፈቃድ መታተሙን የታተሙት መጻሕፍትና ዛሬም በሕይወት የሚገኙት የመጻሕፍቱ ደራሲዎች ምስክሮች ናቸው ።

ምናልባት ማኅበርተኞቹ ሲኖዶስን መስማትና መከተል ስለማይፈልጉና ለቅዱስ ሲኖዶስም ካላቸው ንቀት የተነሣ እንደማያይ እንደማይሰማ በመገመትና በንቀት የተነሰነዘረ ነገር ነው ። እስኪ ማን ይሙት የኤጲስቆጳሳት ሢመትና ሢመተ ፓትርያርክ በሚከናወንበት በቅድስት ሥላሴ ካቴድራል 1940ቹ ጀምሮ እስከ 1986 ዓ/ም ቤተ ክርስቲን ስትገለገልበት ፣ ስታወድስበት ሲኖዶስ ሳያውቅ ነው ማለት ከስድብ የከፋ ስድብ አይደለምን ? ንጉሡ ከተገደሉ ፥ ሊቀ ሥልጣናቱም ከታሰሩ በኋላስ አርጋኖኑ መቸ አገልግሎቱ ተቋረጠ ? ። ታሪክ ይታዘባልና ወንዶሞቻችን በቤተ ክርስቲያን ላይ የሐሰት ምስክር ባይሆኑ መልካም ነው።

  1. በአርኖን መዘመር መናፍቅነት ነው ይላሉ ።

ትክክል አይደለም ፤ የቤተ ክርስቲያን ታሪክ እንደሚያስረዳው ፣ በሠለስቱ ምዕት ዘመን ፣ በዘመነ ቈስጠንጢኖስ /በቢዛንታይን ዘመነ መነግሥት/ ቤተ ክርስቲያን ትጠቀምበት የነበረ ነው ። አኀት አብያተ ክርስቲያናትና ሌሎችም አብያተ ክርስቲያናት ይዘምሩበታል ።

በአርጋኖን መዘመር ያስፈለገው በእኛና በፕሮቴስታንቶች መካከል ያለውን አጥር አፍርሶ አንድ ነን ለማለት ነው ይላሉ ።

ሐሰት ነው ለምሳሌ በሀገራችን የምትገኝ የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን የእኛን ያሬዳዊ መዝሙርና የእኛን ዜማና የመዝሙር መሣያ ነው የምትጠቀመው ፣ ግን ከእኛ ጋር አንድ አላደረጋትም ። ግብጾች አርመኖች ሶርያዎች ካቶሊኮች ኦርቶዶክሱ ዓለም በሙሉ በአርጋኖን ይዘምራሉ ፕሮቴስታት ጋር አንድ ለመሆን መንገድ ለመጥረግ ፈልገው ነውን ? አይደለም ። አንድን ቤተ እምነት ከሌላው ቤተ እምነት የሚለየው ትምህርተ ሃይማኖት /ዶግማ/ ነው እንጂ የመዝሙር መሣሪያ አይደለም ። ነገር ግን የእኛ የቤተ ክርስቲያን ተቆርቋሪዎች በጉልበት እንጂ በእውቀት ፣ በጠብ እንጂ በፍቅር ፣ ባለመቀበል እንጂ በመቀበል ፣ በመበተን እንጂ በመሰብሰብ ስለማያምኑ ነው ።

  1. አንድ አንድ ሰዎች ሲኖዶስ ሳይወስን አንድ አባት ተነ ርጋኖን ዘምሩ ብሎ ማወጅቀኖናዊነት አይደለም  ቀኖናዊነት ከሌለ ኦርቶዶክሳዊነት የለም ይላሉ ። በአርጋኖን እንዲዘመር የሀገር ቤቱ ሲኖዶስም የውጭ አሀገር ሲኖዶስም የከለከበት ወቅት የለም ።የአዲስ አበባው ቅዱስ ሲኖዶስ በ1986 ዓ/ም በግንቦት ወር ባደረገው ጉባኤ «በዋሽንት ፥ በከበሮ ፥ በጸናጽል ፥ በመሰንቆ ፥ በበገና ፥ በእምቢልታ ፥ በአርጋኖን ብቻ እንድንጠቀም አዝዟል» ይላል ። [16]

ከዚያ ቀጥሎ ማቅ አቋሙን ሲገልጥ «ከዚህ ወጥቶ በኦርጋን ልዘምር የሚል ካለ የቤተ ክርስቲያኒቱ አባል አይደለም ይላል ። ከዚህ የምንማረው ቤተ ክርስቲያን አርጋኖንን ከመዝሙር መሣሪያዋ ውስጥ ማጠቃለሏን ነው ።

ነገር ግን የቤተ ክርስቲያንን ልሳን የማያውቀው ማቅ አርጋኖን ኦርጋን መሆኑን ባለማወቅም ይሁን በክፋት ውሳኔውን የሚጻረር ቃል ማስተላለፉን ልብ ይሏል ።  እንዲሁም የማቅ አቋም በአርጋኖን /ኦርጋን/ መዘመር አንቀጸ ሃያማኖት ሁኖ ሰውን ከቤ/ክ እንደሚለይ ያሚያምን የቤተ ክርስቲያን እዳ መሆኑን ነው ። ኦርጋኖን ጠቅላላ የመዝሙር መሣሪያዎችን የሚወክል በመሆኑ መሣሪያ ለማለት በመዝሙረ ዳዊት 150 ላይ ተጠቀሰ እንጂ አንድ አይነት መሣሪያን አያመለክትም ይላሉ ።

ይህ አያጣላንም ፣ አርጋኖን ብዙ መሣሪያዎችን የያዘ ብዙ አይነት ድምጽ የሚሰጥ መሣሪያ ስለ ሆነ ነው ።

  1. በአርጋኖን በመዘመሩ ምክንያት አስቷቸው ወደ መናፍቃን የገቡ አሉ ። [17] የሚለው የማቅ ሰባኪ አባባል እውነትነት አለውን ?

የለውም ። ማኅበረ ቅዱሳን በዱላ ደብድቦ በር አዘግቶባቸው ፍትሕ አጥተው መጥፋታቸውን ረስተውት ይሁናል ። በእውነት የቤተ ክርስቲያን ልጆች ወደ መናፍቃን ያፈለሳቸው የዚህ ቡድን ዱላ ነው እጂ አርጋኖን አልነበረም ።

ማጠቃለያ

ምክንያታዊና መጽሐፋዊ የሆነውን ነገር እስካልተከተልን ድርስ መቼም ቢሆን መነቃቀፉ አይቆምምና ። በቡድን መነዳቱን ትተን የቤተ ክርስቲያን መጻሕፍት ምን ይላሉ ። አባቶቻችንስ ምን ይላሉ እንበል ።ከመፍረድ በፊት መስማትና ማየት ይቅደም ፣ በፈረድንበት ፍርድ የሚፈረድብን ስለ ሆነ ።

መነቃቀፉ ቀርቶ የምንነጋገርበትን ርእስ በተመለከተ መጻሕፍትን መሠረት አድርገን የጋራ መድረክ ተፈጥሮ መነጋገር ሲገባ ፣ ለምን በዓለም መድረክ ቤተ ክርስቲያንን እየነቀፉ ምእመናንን እያሳፈሩ ሥርዓተ  ቤተ ክርስቲያንን እየናዱ መኖርን እንደ ፈቀዱ አይታወቅም ።

አርጋኖን የመጽሐፍ እንጂ የመሣሪያ ስም አይደለም ማለት ትክክል ነውን ?

ትክክል አይደለም ።

አርጋኖን ድምጽ ነው እንጂ መሣሪያ አይደለም ማለት ትክክል ነውን ?

ፈጽሞ ትክክል አይደለም ።

አርጋኖን ኦርጋን አይደለም ማለትስ ምክንያታዊ ነውን ?

ምክንያታዊ አይደለም ።

በኦርጋን መዘመር ኢቀኖናዊነት ነው ማለት ተገቢ ነው ?

ተገቢ አይደለም ።

በኦርጋን የዘመሩም ሆነ ያዘመሩ የሃያማኖት ሕጸጽ አለባቸው የሚለው የማኅበረ ቅዱሳን ሰባክያን አቋም ትክክል ነውን ?

ፈጽሞ ትክክል አይደለም ።

ለቤተ ክርስቲያን የሚያስብ ሁሉ በጳውሎስ ዘመን እንደ ነበሩት ቤተ ክርስቲያንን ይበጠብጡ እንደ ነበሩ ፥ ቅዱስ ሉቃስ «ምናምንቴዎች» ብሎ እንደ ጠራቸው አይሁዳውን ቢጽ ሐሳውያን ፣ ቤተ ክርስቲያንን ሰላም ለሚነሡት ግለሰቦች ላስተላልፈው የምፈልገው ነገር ከዚህ የሚከተለውን ነው ።

መደማመጥ ይኑር ። አባቶችንም ምእመናንንም ግራ አታጋቡ ። ለሕዝቡ ሰላም አስቡለት እንጂ የግል ችግራችሁን የቤተ ክርስቲያን ችግር አድርጋችሁ አታቅርቡ ። የመደብ ትግሉ ከአውደ ምሕረት ይወገድ ። የሥጋ የሥራ መስክ በቤተ ክርስቲያን ለመፍጠር ሥጋውያኑም መንፈሳውያን ነን በሚል ፍጹም በቤተ ክርስቲያን ቅዱሳን ባልተገለጠ የድፍረት ሥራ በመሥራት ለዕለታዊ ጥቅምና ክብር ብላችሁ ቤተ ክርስቲያንን አትውኳት ። ዐይነ ልቦናችሁ ይብራ ። ሌሊቱ አስተሳሰብ ጐህ ይቅደድበት ። ጨለማ ይወገድ አለማወቅም ይራቅ ። ሞቱ ሕይወት ሕይወቱም ሞት ፣ ጽድቁ ኃጢአት ኃጢአቱም ጽድቅ መስሎ አይታያችሁ ።

ተስማምተን ተሰብስበን በፍቅር እናምልክ እንዘምር ። ክርስቶስ ለሞተለት ሕዝብም እናስብለት ። በተራ ውዝግብ ቤተ ክርስቲያንን የሁከት አደባባይ አታድርጓት ። ስለዚህ የቤተ ክርስቲያንን አሥራት ጅራፏን ከቤተ ክርስቲያን ነጥቀው ቤተ ክርስቲያንን በገንዘቧ የሚገርፏት የጥቅም እና የንግድ ሐዋርያት አገልግሎት ይቁም  እንላለን።

የዳዊት ልጆች ሆይ  ሜልኮልን አትስሟት ። ዝም በሉ ብትል ወይም ብትስቅባችሁ ሜልኮል ዓለምን እርሷት ። ዝም ብላችሁ ዘምሩ ። እሷም ትመክናለች ። የንጉሡ የክርስቶስ አባት የሆነው የሰሎሞን እናት እንዳትሆንም በምክንያት ትቀጣለች ። ወደ መቃብር ትወርዳለች ። ከክርስቶስ ቤተሰብ ቍጥርም ውስጥ አትገባም ። ግብዝነቷ ያጠፋታል ።

ጥቅም ያሳወራት ያሰከራት የአንድ አንድ ክርስቲያን መሰል ቢጽ ሐሳውያን ወጣቶች ልብ ሜልኮልን ደስ ባይላትም ቤተ ክርስቲያን በሚቻላት መንገድ ሁሉ ፈጣሪዋን ታመልካለች ። ለምስጋና ተፈጥራለችና ።

ወስብሐት ለእግዚአብሔር ……. አሜን

መጋቤ ሐዲስ መምህር ልዑለ ቃል አካሉ

www.zenatewahedo.org

[1] አቡነ ማትያስ ለቤተ ክርስቲያኒቱ የትምህርት ተቋማት ያስተላለፉት ደብዳቤ ላይ እነዚህ ነጥቦች ሁሉ ተጠቅሰዋል።

[2] ሐመር ኅዳር/ታኅሣስ 1995 የታተመው የማቅ መጽሔት ገጽ 39

[3] የአለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ የግእዝ መዝገበ ቃላት ይመልከቱ ገጽ 239

[4]  (Organ History page 2-5)    641

ዓዲ http://faculty.bsc.edu/jhcook/orghist/history/hist001.htm

[5] ዚቅ የጥር ዮሐንስ ወልደ ነጐድጓድ እስመ ለዓለም ።

[6] አርያም ዘቅዱስ ያሬድ የማክሰኞ ገጽ 152

[7] ጥንታዊ ሥርዓተ ማኅሌት ዘአቡነ ያሬድ ሊቅ  የሚለውን መጽሐፍና ገድለ ያሬድን ተመልከት

[8] Orhtodox Dictionary of The Christian Church page 1192

[9] መጽሐፈ አርጋኖን ገጽ 11-12 ይመልከቱ

[10] ሐመር ኅዳር/ታኅሣሥ 1995 የታተመው የማቅ መጽሔት ገጽ 39

[11] Orhtodox Dictionary of The Christian Church page 1192

[12] ስንክሳር መስከረም 18 ወበዛቲ ዕለት ገብረ ተአምረ ቶማስ ከሚለው ላይ ተመልከት ።

[13] «በስመ ማኅደር ይጼዋእ ሀዳሪ ወበስመ ኅዳሪ ይጼዋእ ማኅደር » እንዲል።

[14] ዳንኤል ክብረት ከሐራ ጥቃዎች ጋር ካደረገው ቃለ መጠይቅ የተወሰደ

[15] ዐባይነህ ካሴ ከሐራ ጥቃዎች ጋር ካደረገው ቃለ መጠይቅ የተወሰደ ።

[16] ሐመር ኅዳር/ታኅሣሥ 1995 የታተመ የማቅ መጽሔት ገጽ 39

[17] ቀሲስ ደጀኔ በኢንተርኔት ካሰራጨው ጽሑፍ የተወሰደ

The post በኦርጋን የመዘመሩ ጉዳይ | መዝሙርና የመዝሙር መሣሪያዎች appeared first on Zehabesha Amharic.


እጮኛውን ደብድቦ ከእንግሊዝ ወደ ኢትዮጵያ የተሰደደው ግለሰብ በ 15 አመት እስራት ተቀጣ

$
0
0

fikirgna 1

“ከ እስራት ስወጣ አንቺን ሆነ ቤተሰቦችሽን አልምራችሁም ብሎ ዝቶብኛል” ከሳሽ የሰጠችው ቃል

ከታምሩ ገዳ

የ33 አመቱ ጎልማሳ ማሃድ ኢዳን እና ስሟ ለጊዜው ያለተገለጸው የ 20 አመቷ እጮኛው ቀደም ባለው ቅራኔያቸው ሳቢያ ማሃድ ከ እንግሊዝ ፖሊሶች የክስ ፋይል ውስጥ የወድቃል ። ማሃድም ይህንን ከሁለት አመት በፊት የተደርገ ቅራኔን እና የክስ ፋይል ውድቅ እንዲሆንለት እጮኛው አንድ መወጫ ዘዴ ካላፈላለገች ብቸኛው መፍትሔ የአርሷ ህይውትን ማጥፋት ብቻ አንደሚሆን ይዝታል፣ ያሰፈራራታልም እንደ ከሳሽ እማኝነት ቃል እና የፖሊስ ሪፖርት ዘገባ።

fikrgnaከ ዋና መዲናይቱ ሎንዶን በማእከላዊ ምእራብ አቅጣጫ ከምትገኘው በኮቨንተሪ ከተማ ውስጥ ነዋሪ የነበረው በትውልዱ የጎረቤት ሶማሊያ ተወላጁ ማሃድ የቀደሞው የሴት ጓደኛውን ቀደም ባለ ግጭት ሳቢያ ከፊቷ ላይ በቡጢ በመማታት ለቀረበበት የፖሊስ የክስ ቻርጅ ወድቅ እንድታስደርግለት፣ አሊያም እንደሚገድላት ይዝትባታል ። የፍላጎቱ ያለመሳካት ያሰጋው እና ያበሳጨው ተከሳሹ ማሃድ የቀደሞ ጓደኛው ባለፈው መሰከረም 2013 አኤ አከ አንድ የመኪና ማቆሚያ (ፓርክ )ውስጥ ከመኪናዋ ውስጥ ሳለች በቢላ ካጠቃት በሁዋላ ወደ ኢትዮጵያ “እግሬ አውጪኝ” በማለት በኢትዮጵያ ውስጥም ደብዛውን በማጥፋት ለሁለት አመታት ይደበቃል።

ከዚያም በሁዋላ ክሱ ተረሳስቶልኝ ይሆናል ከሚል ሕሳቤ ወደ እንግሊዝ ለመመለስ ከኢትዮጵያ ወደ እንግሊዝ ምድር ሊያስገባው የሚችለው የመግቢያ ቪዛን ለማግኘት ኢትዮጵያ ውስጥ ሲያመለክት ፖሊስ በምደረ እንግሊዝ ውስጥ ሲያሰሰው የከረመው እና በወንጀለኞች የአሰሳ መዝግብ ( ክራይምስ ዎችስ ) ውስጥ ስሙ የተካተተው ማሃድ ባለተጠበቀ ሁኔታ የት እንደሚገኝ ለእንግሊዝ ፖሊሶች ትልቅ ፍንጭ ሰጣቸው ። ፖሊሶቹም ግለሰቡ ወደ እንግሊዝ ተመልሶ እንደሚ መጣ በተሰፋ እና በምስጢር ሲጠባበቁት ቆይተው ባለፈው ነሃሴ 2015 እ ኤ አ ከ ሎንዶኑ አለማቀፉ የሂትሮው አውሮፕላን ጣቢያ እንደደረሰ ከ እጃቸው ወድቋል።

እንደ ኮቨንተሪ ቲሊግራፍ ጋዜጣ ዘገባ ከሆነ ክሱን በሕግ ጥላ ስር ( በ እስር ቤት ) ሆኖ ሲከታተል የቆየው ተከሳሹ ማሃድ ሰሞኑን በዋለው ችሎት የቀደሞ የሴት ጉደኛውን በቡጢ በመማታት እና እካላዊ ጉዳት በማድረስ ፣ አጮኛውን በቢላዋ ለመግደል በመሞከሩ ፣ የአይን እማኞችን በማሰፈራራት ፣ የተከለከለ መሳሪያ (ቢላዎ )በሕዝዊ ስፍራ( አደባባይ )ይዞ በመገኘቱ እና የህግ አግባብን ለማዛባት ሲል አገር ጥሎ ወደ ኢትዮጵያ በመሰደድ ባደረጋቸው ጥፋቶቹ ተከሶ ግለስቡም ለ ቀረቡበት ክሶችን ጥፋተኛነቱን በማመኑ የ11 አመት እስራት ለሕዝብ ደህንነት (ጥበቃ) ሲባል የተጨማሪ 4 አመታት በድምሩ የ 15 አመት እስራት ተፈርዶበታል።
በአንድ ወቅት የልብ እና የፍቅር ጭምር ጓደኛው የነበረችው በሁዋልም ለተደራራቢ በደሎች የተዳረገችው የቀደሞ እጮኛው ከ ፍርድ ቤቱ ወሳኔው በሁዋላ ለዜና ሰዎች በሰጠችው አስተያየት”መቼም ይሁን መቼ ከእስራት ሰወጣ አንቺን አገድላለሁ፣ አንቺን ባጣ እንኳን ቤተሰቦችሽን እልምራቸውም በማለት ዝቶብኛል።” ስትል ግለሰቡ በእርሷ ላይ ያሳደረውን አካላዊ እና ስነልቦናዊ ጉዳት ፣ በቤተሰቦቿ ላይም የጣለውን ስጋት ገልጻለች።ታዲያ የህግ ታራሚው ሃማድ እስራቱን ሲጨርስ ዛቻውን ተግባራዊ ያድርገው አሊያም በተቃራኒው ከእስራቱ በመታረም ጥሩ ዜጋ በመሆን ወደ ማሕበረሰቡ ስለ መቀላቀሉ ጊዜ የሚፈታው ጉዳይ ይሆናል።

The post እጮኛውን ደብድቦ ከእንግሊዝ ወደ ኢትዮጵያ የተሰደደው ግለሰብ በ 15 አመት እስራት ተቀጣ appeared first on Zehabesha Amharic.

እነ ብርሃኑ ተ/ያሬድ ተከላከሉ ተባሉ *ተከሳሾች 200 የሰው መከላከያ ምስክሮች አሉን ብለዋል

$
0
0

በነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተር

tekele Yaredየኢትዮ-ኤርትራ ድንበርን አቋርጠው ኤርትራ የሚገኘውን የአርበኞች ግንቦት ሰባት ወታደራዊ ክንፍ ሊቀላቀሉ ከአዲስ አበባ ተነስተው ሲጓዙ ማይካድራ የሚባል የድንበር ከተማ በቁጥጥር ስር መዋላቸውን ጠቅሶ የፌደራል አቃቤ ህግ የሽብር ክስ የመሰረተባቸው እነ ብርሃኑ ተ/ያሬድ እንዲከላከሉ ብይን ተሰጥቷል፡፡

ዛሬ የካቲት 4/2008 ዓ.ም ፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 14ኛ ወንጀል ችሎት የቀረቡት ተከሳሾቹ አቶ ብርሃኑ ተ/ያሬድ፣ ወ/ሪት እየሩሳሌም ተስፋው፣ አቶ ፍቅረማርያም አስማማው እና አቶ ደሴ ካህሳይ አቃቤ ህግ ያቀረበባቸውን ክስ በሰነድና በአንድ የሰው ምስክር ማስረጃዎች አስረድቷል በሚል ተከሳሾች መከላከል ይገባቸዋል ሲል ፍርድ ቤቱ ወስኗል፡፡

ተከሳሾች 14ኛ ወንጀል ችሎት እንዲቀየርላቸው አቤቱታ አቅርበው እንደነበር በማስታወስ ይህ ጉዳይ እልባት ሳያገኝ ችሎቱ ብይኑን እንዳያሰማ ቢጠይቁም፣ ችሎቱ ‹‹አቤቱታው ቶሎ ብይን እንዲሰጣችሁ የሚጠይቅ ነው፣ በመሆኑም ብይኑ ተሰርቷል›› ሲል መልስ ሰጥቷል፡፡ በዚህም ተከሳሾች ብይኑ አይሰማብን የሚለውን ጥያቄ ባለመቀበል ችሎቱ ብይኑን በንባብ አሰምቷል፡፡

እነ ብርሃኑ ተከላከሉ መባላቸውን ተከትሎ መከላከያ ማስረጃዎች ያቀርቡ ከሆነ በሚል ፍርድ ቤቱ ጠይቆ፣ ተከሳሾች 200 የሰው ምስክሮችና የሰነድ ማስረጃዎች በጋራ እንደሚያቀርቡ አስታውቀዋል፡፡ ፍርድ ቤቱም መከላከያ ማስረጃዎችን ለማድመጥ ለመጋቢት 21/2008 ዓ.ም ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡

በሌላ በኩል ተከሳሾች እያዘጋጁት የነበሩት የተከሳሽነት ቃል ጽሁፍ በማረሚያ ቤት ፖሊሶች እንደተወሰደባቸው ለፍርድ ቤቱ በመግለጽ ከዚህም በኋላ ተመሳሳይ ለችሎት የሚቀርቡ ማስረጃዎችን ማዘጋጀት እንዲችሉ ለማረሚያ ቤት ትዕዛዝ እንዲሰጥላቸው ጠይቀዋል፡፡

በተመሳሳይ ችሎት የቀረቡት እነ መቶ አለቃ ጌታቸው መኮንን እና እነ መቶ አለቃ ማስረሻ ሰጠኝ 14ኛ ወንጀል ችሎት እንዲቀየርላቸው አቤቱታቸውን በጽሁፍ አቅርበዋል፡፡ ፍርድ ቤቱም የቀረበውን አቤቱታ መርምሮ ብይን ለማሰማት ለየካቲት 10/2008 ዓ.ም ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡

The post እነ ብርሃኑ ተ/ያሬድ ተከላከሉ ተባሉ *ተከሳሾች 200 የሰው መከላከያ ምስክሮች አሉን ብለዋል appeared first on Zehabesha Amharic.

Health: በኤድስ የሞተው አጎቴ እንዴት ኤች.አይ.ቪ የለበትም ተባለ??!

$
0
0

‹‹የ65 ዓመት አጎቴ ያሳድገኝ የነበረ ሲሆን በተለያየ ጊዜ በገጠመው ህመም ሳስታምመው ቆይቻለሁ፡፡ ይሁን እንጂ ሊሻለው ባለመቻሉ ከፍተኛ ህክምና እንዲደረግለት ወደ አዲስ አበባ ሪፈር ተደረገ፡፡ ሆኖም በተደረገለት ምርመራ ከኤድስት ጋር የተያያዘ እንደሆነና ነገር ግን ለዚህ በሽታ የሚያጋልጥ ኤች.አይ.ቪ እንደሌለበት ነበረ የተረጋገጠው፡፡ በመጨረሻ ግን የካንሰር ህመም እንዳለበት ነገር ግን ህመሙ በመሰራጨቱ ሊድን እንዳልቻለ ነበር የተረዳነው፡፡ በአሁኑ ወቅት ካረፈ ስድስተኛ ወሩ ቢሆንም የህመሙ ጉዳይ ቢከነክነኝ ነው ይህን ደብዳቤ ወደ እናንተ የላኩት፡፡ ለመሆኑ አንድ ሰው ኤች.አይ.ቪ ሳይኖርበት እንዴት ኤድስ ሊኖርበት ይችላል? ካንሰርና ኤድስ ምን አገናኛቸው? እባካችሁ መልሳችሁን በጉጉት እጠብቃለሁ፡፡

አስቴር ወላንሳ

ask your doctor zehabesha

ጥያቄሽ በራሱ አነጋጋሪነት ያለውና ለሌሎችም የሚያስተምር በመሆኑ ቅድሚያ ሰጥተነዋል፡፡ በዋናነትም ጥያቄሽ ኤች.አይቪ በሌለበት ሁኔታ እንዴት አንድ ሰው ኤድስ ሊኖርበት ይችላል? የሚል በመሆኑ በሁለቱ ረገድ ያለውን ትስስር እንዲህ እናቀርበዋለን፡፡

ኤድስ የሰውን ልጅ የበሽታ መከላከያ አቅም በማመንመን በተለይም የነጭ ህዋስን የተባለውን ከሰውነታችን ስለሚያጠፋው (ስለሚገለው) በዛ ያሉ በሽታዎች በቀላሉ በሰውነታችን ጤናማ አካል በነበረበት ወቅት በቀላሉ ሊያስወግዳቸው ይችል የነበሩትም በሽታዎች ለምሳሌ እንደ ቲቢ ያሉ በሽታዎች በቀላሉ በሰውነታችን ውስጥ ይሰራጫሉ፡፡

ማንኛውም ቅስም ሰባሪ በሽታ ኤድስ ብሎ መጥራት ይቻላል? ማንኛችንም ቅስም ሰባሪ በሽታ ኤድስ ብለን መጥራት አንችልም፡፡ ከዚህ በፊት የነበሩ ነባር ቅስም ሰባሪ በሽታዎች አሉ፡፡ ለመጥቀስ ያህል ካንሰርና የስኳር በሽታ፡፡ ከመድሃኒቶችም ቅስም የሚሰብሩ በሽታዎች አሉ፤ ለምሳሌ ያህል ለአስም በሽታ ፍቱን የተባለ መድሃኒት እንዲሁ ከልክ በላይ ከተወሰደ ማለት ሐኪም ካዘዘው በላይ ከተወሰደ ወይም ያለማቋረጥ ለረጅም ጊጊ ከተወሰደ እንዲሁም ለሌሎችም በተፈጥሮ ጉድለት የሰውነት የመከላከያ ንጥረ ነገር ሊጎድልም ይችላል፡፡ እንደ ኤች.አይ.ቪ ኤድስ ተመሳሳይ የበሽታ ምልክቶችን የሚጋሩ ህመሞች ግን አሉ፡፡ ለምሳሌ እንደ ስኳር፣ አስም፣ ቲቢ፣ ካንሰር፣ ከፍተኛ የምግብ እጥረት፣ በተፈጥሯቸው የበሽ መከላከያ ኃይላቸው የደከመባቸው፣ የአዕምሮ ህመምና የመሳሰሉት ናቸው፡፡

ኤድስን ከሌሎች ኤድስ መሰል ህመሞች የምንለየው እንዴት ነው? ኤች.አይ.ቪ የሚመጣውን ኤድስን ከሌሎች ኤድስ መሰል ህመሞች የሚለየው በኤድስ የሚከሰተው ቅስም ሰባሪነት የሰውነት የበሽታ መከላከያ ሴሎችን ሙሉ ለሙሉ ስለሚደመስሰው ሰውነታችንን በቀላልም ሆነ ለከባድ ህመም ሙሉ በሙሉ ስለሚያጋልጠው ነው፡፡ እንዲሁም የሰውነታችን ዋና ዋና አካላት (ልብ፣ አዕምሮ፣ ኩላሊት) የሥራ መስተጓጎል፣ ሰውነትን በሙሉ ስለሚበታትነውና ስለሚያደቀው ለከፍተኛ ክሳት፣ በከፍተኛ በሽታ መጋለጥ፣ ለማይቋረጥ ተቅማጥ፣ ለማይቋረጥ ትኩሳት፣ ከፍተኛ ለሆነ ምግብ የማስጠላት፣ የማስታወክ፣ ጠቅላላ የቆዳ መቁሰል፣ የምላስ መገንተር እንዲሁም በጣም መድከምና የመሳሰሉትን ያስከትላል፡፡ ነገር ግን በሌሎች ኤድስ መሰል በሽታዎች እነዚህ ሁሉ ምልክቶች አይከሰቱም፡፡ በተጨማሪም ሌሎች መሰል ህመሞች በቀላሉ ታክመው የሚድኑ ናቸው፡፡ እነዚህ ህመሞች ወደ ኤድስ መሰል ህመምነት የሚሸጋገሩት እስካልታከሙ ድረስ ነው፡፡

የኤች.አይ.ቪ ምርመራ በአንቲቦዲ ቴስት ላይ ያተኮረ ነው፡፡ በተፈጥሯቸው የአንቲ ቦዲ እጥረት ያለባቸው ሰዎች አሉ፡፡ እነዚህ ሰዎች በኤች.አይ.ቪ ቢያዙ ምርመራቸው ኔጌቲቭ ሊሆን ይችላል፡፡ እንዲሁም ኤድስ መሰል ህመሞችን ይባላል፡፡ ኤች.አይ.ቪ ፖዘቲቭ መሆኑን በከፍተኛ ደረጃ የሚያረጋግጥ (Sensitivity)፣ ኤች.አይ.ቪ ኔጌቲቭ መሆኑን በከፍተኛ ደረጃ የሚያረጋግጥ (Sensitivity) ምርመራ አለ፡፡ ቀድሞውንም ቢሆን ማለት በሽታው ባለባቸው ወይም በሌለባቸው ላይ ይህ ‹‹የአንቲቦዲ ቴስት›› ፀረ ህዋስ የመከላከያ አካል መቶ በመቶ አለ መቶ በመቶ በሽታው ፖዘቲቭ ወይም መቶ በመቶ የለብህም ኔጌቲቭ ማለት አይቻልም፡፡ ይህ የሁሉም የላብራቶሪ ቴስቶች የውስጥ ባህሪ ተቀባይነት ያለው ስህተቶች አሏቸው፡፡ ይህም የላቦራቶሪ ውጤት መቶ በመቶ ትክክለኛ ባይሆንም ሳይንቲስቶች ወደ ትክክለኛው ቴስት የሚያቀራርቡበት ዘዴ አላቸው፡፡ ይህም ዘዴ የአንድን በሽታ በትክክለኝነት የሚያረጋግጥ ነው፡፡ ለምሳሌ ኤች.አይ.ቪ ፖዘቲቭ መሆኑን በከፍተኛ ደረጃ የሚያረጋግጥ ቴስት (Sensitivity) ይባላል፡፡ በአንፃሩ ደግሞ በሽታው እንደሌለ ኤች.አይ.ቪ ኔጌቲቭ መሆኑን በከፍተኛ ደረጃ የሚያረጋግጥልን ቴስት (Specificity) ይባላል፡፡ እነዚህን በሚያሟሉ መመርመሪያዎች በመጠቀም ወደ እውነታው መቅረብ ይቻላል፡፡ እንጂ በአንዴ የአንቲቦዲ ምርመራ ብቻ አንድን ሰው ሙሉ በሙሉ በሽታው አለብህ የለብህም ማለት አይቻልም፡፡ ይህንንም ለማስተካከል ቴስቱን መደጋገም ወይም ዌስተርን ብሎት የሚባለውን ምርመራ ማድረግ ወይም እራሱን ኤች.አይ.ቪ ቫይረሱን በማሳደግ በሽታውን ማረጋገጥ የሚቻልበት መንገድ መጠቀም አለብን፡፡

አንዳንድ ጊዜ ቫይረሱ በደማቸው ውስጥ ሳይኖር ነገር ግን በምርመራ ፖዘቲቭ የሚሆኑበት ምክንያትም አለ፡፡ ይህ ከላይ ከጠቀስኩት ማብራሪያ ጋር ሊያያዝ ይችላል፡፡ ለምሳሌ ሰውነታችን ለሌሎች መደበኛ በሽታዎች ለምሳሌ ለወባ እንኳን የሚፈጥረው ፀረ ህዋስ አካል (Antibody) ለኤች.አይ.ቪ ፖዘቲቭ የሚሆንበት ጊዜ ነበር፡፡ ይህም ማለት ቫይረሱ በደም ውስጥ ሳይኖር ይህ የሆነበት ምክንያት ቴስቱ አንቲቦዲን ማግኘት እንጂ ይህ የኤች.አይ.ቪ አንቲ ቦዲ ነው፡፡ ይህ የወባ አንቲ ቦዲ ነው ብሎ ስለማይለይ ነው፡፡ በተለይ በመጀመሪያ የአንቲቦዲ ቴስት በተጀመረበት ወቅት የተከሰተ ችግር ነበር፡፡ በአሁኑ ጊዜ ግን ቴስቱ እየጠራ ስለመጣ ይህ መሰል መደበላለቅ አይታይም፡፡

በመሆኑም ኤድስ ማለት የሰውነትን የበሽታ መከላከያ ኃይል በማመንመን ሰዎችን ለተለያዩ ህመሞች የሚያጋልጥ ክስተት ሲሆን ይህን መሰል ችግር ከሚፈጥሩ መንስኤዎች ውስጥ ታዲያ አንዱ ኤች.አይ.ቪ ነው፡፡ እሱ ብቻ ግን አይደለም፡፡ ለምሳሌ አጎትሽ የሞቱበት ካንሰርም ይኸው ባህሪ አለው፡፡ በመሆኑም የአጎትሽ ህመም በመጀመሪያ ከኤድስ ጋር በተያያዘ ቢጠረጠሩምና ለዚህም ኤች.አይ.ቪ በዋናነት ተጠርጥሮ ከተመረመረ በኋላ ኔጌቲቭ ቢሆንም ይህን መሰል ህመም በካንሰርም ሊመጣ እንደሚችል መረዳት አለብን፡፡ ይህም ማለት ኤድስ መሰል ህመም የሚታይበት ሰው ሁሉ በኤች.አይ.ቪ ተይዟል ማለት እንደሌለብን አንዱ ማሳያ ነው፡፡ መንስኤው ሌላም ሊሆን ስለሚችል መጠርጠር ያስፈልጋል፡፡ በተረፈ የሞቱትን ነፍስ ይማር፤ እናንተንም እግዜር ያጥናችሁ ማለት እወዳለሁ፡፡ ሰላም!

The post Health: በኤድስ የሞተው አጎቴ እንዴት ኤች.አይ.ቪ የለበትም ተባለ??! appeared first on Zehabesha Amharic.

የኢትዮጵያ የራብ ጽጌረዳዎች |‘በሰው መከራ የተመረቱ አበቦች ከአውሮፓ ገበያ ይደርሳሉ’በሚል ርእስ ከተጻፈ የእግሊዝኛው ጽሁፍ ትርጉም

$
0
0

red  roses

የእግሊዝኛው ጽሁፍ ደራሲ ዓለም ተሰማ ተርጓሚው ቢላል አበጋዝ
የራብ ጽጌረዳዎች

አዲስ አበባን ሁሪያዋን በመኪና እየዞሩ ቢያይዋት በተርታ የተደረደሩት በፕላስቲ የተሸፈኑት የአውሮፕላን ጋራጅ የመሰሉትን ቤቶች ማንም አያጣቸውም። ቀረብ ብሎ ላያቸው ደግሞ ለምን እንደተሰሩ ምን እንደሚከናውንባቸው መለየት ያስችለዋል። አበባ ተመርቶ ለገበያ የሚቀርብባቸው ናቸው፤ለዚያውም ለአውሮፓ ህብረት ። የአበባው ኢንዱስትሪ ህወሃት መሩ መንግስት ልማት ሰራሁ ብሎ የሚፏልልበት ነው። ዛሬ እንዲህ ያሉ ሰባ ዘጠኝ3 እርሻዎች ይገኛሉ።ከእኒህ ከሩቁ አንጸባራቂ ከሆኑት የአበባ ማምረቻ ቤቶች በተረፈ ሜዳ ላይ የተንሰራፉም ሌሎች እርሻዎች ይገኛሉ።

ህወሃት መሩ መንግስት እያበበ ስላለው የአበባ ኢንዱስትሪ ቢያወራም ተጨባጩ ሁኔታ ሌላ ነው።አጥፊ ውጤቱ ዜጎችን የበደለ፤ አየር ንብረቱንም የበከለ ነው። ይህ ደግሞ ሊደበቅ የማይቻል ነው።ሰዎች ከመሬታቸው ተፈናቅለዋል። የመጠጥ ውሃ በሚጎዱ መርዞች ተበክሏል።ሰዎች ለረጅም ሰዓታት በመስራት ይበዘበዛሉ።ይህ ለጥቂቶች ሲሳይ ለብዙሃን ስቃይ የሆነን አሳዛኝና አፋኝ የፖለቲካ ና የኢኮኖሚ ውጥረት ነው። ዛሬ በኢትዮጵያ ህዝብ ድምጽ የለውም።በቀበሌ፤ባውራጃ፤ባገር አቀፍም ቢሆን በህወሃት ጨቋንኝ መዳፍ ተይዞ ይገኛል።

ጥቂት ኪሎሜትሮች ሄደት ብዬ አንድ በጭቃ ምርጊት የተሰራ የቆርቆሮ ቤት አገኘሁ።ምርጊቱ ገና የደረቀ አልነበረም።ርጥቡን ጭቃ ነካ እያደረግሁ

“እዚህ መቼ አመጣህ እና እንዴት ሰፈርክ ?” ብዬ ባለቤቱን ጠየቅሁ። “አምስት ቀን በፊት ልጄ ረድቶኝ” አለኝ “ከዚህ በፊትስ የት ትኖር ነበር ?”
“እኔና ቤተሰቤ እዚሁ በዚህ ግድም እንኖር ነበር” “የሞላ ቤት ነበረን። እኔና ባለቤቴ ልጆች እናሳድግበት የነበረ”” “ለምን ታዲያ ቦታችሁን ለቀቃችሁ ?” አስከትዬ ጠየቅሁት።

“በግዳጅ ተፈናቅለን” አለኝ
“ምን ማለትህ ነው ተገደን ስትል ማንስ አስገደደህ?” አልኩት
“በዚች አገር ያልወደድከው እንድታደርግ ማድረግ የሚችል መንግስት ነው” “ለምን እንድትፈናቀል ያደርጋሉ? መሬቱስ ያንተ አይደል? “ አልኩት

“መሬቱማ የኔ ነው እነሱ ግን ለአበባ አምራቾች ሊሰጡት ፈልገው ነው። አበባ አምርተው ውጭ አገር ለመሸጥ ለሚፈልጉ” “ስትፈናቀል ካሳ አግኝተሃል?” እዲነግረኝ ገፋፋሁት።
“ትንሽ ምንዛሪ አንድ በግም የማትገዛ ሰጡኝ። አልቀበልም አልኩ” አለኝ ኔዴቱ እንዳዲስ እየተሰማው።
“መላ ቤተሰቤን ይዠ ጎዳና ላይ መውደቁ ይመራል” አለኝ

“ይህ መሬት ካያት ከቅድማያት የወረስነው። እትብታችን የተቀበረበት። ሁለት ዓመታት ጎዳና ተዳዳሪ ሆንን። ሜዳ ላይ እየተኛን። ለምነን እየበላን።ራሳችንን ችለን እንኖር የነበረ ዛሬ በቀን አንዴም አንበላ። ይህ ለውጥ ኑሮአችንን አሰተጓጎለ ህብረተ ሰባችንን ጎዳ።ለማኞች አደረገን።”

“ማነው በዚህ የሚጠቀም?” አልኩት

“የመንግስት ባለስልጣኖችና ጓደኞቻቸው” አለኝ የድሮ ቤቱን ምስል እያሳየኝ። አያዳመጥሁት ይህ በኔና ቤተሰቤ ላይ ቢደርስ ምን አደርግ ይሆን እያልኩ ባሳብ ዋዠኩ።ባንዴ ሃዘንም ንዴትም ዋጠኝ። ያየሁት በደል በሚሊዮኖች ቤት ተከስቷል።ሃዘን ብቻ ይበቃል ? አልኩት እራሴን።

ብሩክ በመጀመሪያዎቹ ሃያ አመቶችዋ ላይ የምትገኝ ወጣት ሴት ናት።ለሶስት ዓመታት በአበባው ማምረቻ ቤት ሰርታለች።ከስራ ውጭ አግኝቼ ስለ ስራዋ ሁኔታ እንድት ነግረኝ አደረግሁ።

“በአበባው ማምረቻ ቤት ስራሽን ትወጅዋለሽ?” ስላት

ሳቅ ብላ “ምንስ ምርጫ ኖሮኝ” አለችኝ። “ሌላ ስራ የለ ።ያገኘሁት ይሄው ነው።” አለችን በክሰል ምድጃ ቡና እየቆላች። እጆችዋ ላይ አዲስና የቆዩ ቁስሎችን አያለሁ።

“በስራሽ ላይ ነው እንዲህ የቆሳሰልሽው?” አልኳት ወደ ቁስሎችዋ እየጠቆምሁ። “አደጋ መከላከያም የለሽ?” “እንዲያውም “ አለች
“የጅ ጓንት ሆነ ሌላ እንዲው ምንም የለንምን ?” ብዬ አከታትዬ ጠየቅኋት።

“ጤናማ ነበርኩ። ይሄው ዛሬ ግን መተንፈስ ያስቸግረኛል። ይህ የሆነው ስድስት ወራት በአበባው ማምረቻ ቤት ከሰራሁ በኋላ ነው። ሀኪም ቤት ስሄድ በስራሽ የተነሳ ነው ብለውኛል። መተንፈስ ይጨንቀኛል። ቆዳዬን ያሳክከኛል። ያስለኛል።” አለችን ሀዘን በሞላው ገጥታዋ።

የኢትዮጵያው “የራብ ጽጌረዳዎች” በኮንጎ ዴሞክራሲያዊ ሪፑብሊክ ወይም ሴራሊዮን ከሚመረተው “የደም አልማዝ” የተለዩ አይደሉም።ሁለቱም የሰው መከራና ስቃይ ውጤቶች የተፈጥሮ ውድመቶችም ናቸው።ሁለቱም የአምባገነኖች የሃብት ምንጭና መደጎሚያ ናቸው።ባአበባው ሽያጭ የሚገኘው የውጭ ምንዛሪ በዓለምም በአፍሪካ አቻ የማይገኝለት አምባገነን ያነግሳል።ለወያኔ ሲሳይ ነው።ከዚህም በላይ አበባ ማምረቻው መሬት የሚበላ እህል ማምረቻ የነበረ ነው።ስለሆነም ሚሊዮኖች ለራብ ተዳርገዋል።

ጃነዋሪ 26 2016 የተባበሩት መንግስታት የኢትዮጵያን ሁኔታን ሲገልጥ “ቀስ እያ እየቀረበ ያለ ትልቅ አደጋ” ብሎታል። ዛሬ ጦርነት እዳፈራረሳት ሶርያ ያስምስለዋል። “ዛሬ ሁለት ትላልቅ ቅድሚያ የሰጠናችው የአደጋ ቀጠናዎች አሉን።ሶርያ አንደኛ ኢትዮጵያ ሁለተኛ ናት።” ብለዋል ካሮላይን ማይልስ። ማዳም ማይልስ Save The Children የተባለው ህጻናት አድን የተራድኦ ድርጅት ዋና አስተዳዳሪ ናቸው።የኢትዮጵያ ሁኔታ “ቀስ እያ እየቀረበ ያለ ትልቅ አደጋ” ተብሎ ሲገለጥ ህወሃት “ጥጋብ ነው በምግብ ራሳችንን ችለናል” ብሎ በለፈፈ ማግስት ነው።

በሜይ 28 2014 የህወሃት ሃያ አራተኛው የድል በዓል ሲከበር ሀይለ ማርያም ደሳለኝ “ከራብ በመላቀቃችን እንኮራለን።ከዚህ ወዲያ በራብና ጠኔ መታወቃችን ቀርቷል” ብሎ ነበር።

በአፍሪካ ለዘለቄታው የቅኝ አገዛዝ የእርሻ ስራን አመሳቅሎአል።ነፍስ ወከፍ ራሳቸውን የቻሉ ገበሬዎች ተፈናቅለው በትላልቅ ገንዘብ አምንጭ ሰብሎች ለምሳሌ ቡና፤ኮካዎ፤ትንባሆ፤ስኳር፤ጥጥና ጎማ ተተክተዋል።እኒህ ለውጭ ንግድ የሚመረቱ ናቸው። ከበርቴዎችን ቅኝ ገዥዎችን የሚያከብሩ ማለት ነው።በዚህ ሂደት ታዲያ ሚሊዮኖች ደህይተዋል።ካባታቸው መሬት ተፈናቅለዋል። ታሪካቸው ጠፍቷል።ኢትዮጵያ የሚካሄደውም የአበባ እርሻ ምርት ከቅኝ አገዛዙ ልዩነት የለውም።ያው ቅኝ አገዛዝ ያደረገው እየተደገመ ነው። የጥንቱ ቅኝ “አገዛዝ ኋላ ቀር ህዝቦችን ለማሰልጠን” ይባልም ነበር።በ21 ኛው ክፍለ ዘመን ይህን ማለት ያዳግታልና የአሁኑ “ኢንቬትሜንት፤አምራችነት ። ስራ ፈጠራ። ውጭ ባለ ሃብቶች ጋር መስራት” የሚል ስም ይሰጠዋል። ስም እንጂ ልዪነት የላቸውም። ዘመን አመጣሽ ባርነት እንጂ ከዚያ ከጥንቱ ቅኝ አገዛዝ የሚለይ አደለም።

2

በቅርቡ አንድ ጓደኛዬ እንዲህ ብላ ጠየቀችኝ። ይህን እስቲ መልስልኝ አለችኝ። “እንዴት ሁኖ ነው አንድ በባዛት አምሮበት የተመረተ የአበባ ምርት ለአውሮፓ ገበያ ሊያቀርብ የቻለ አገር የራሱን ህዝብ መመገብ ያልቻለበት ?” በተጨማሪ “እንዴት ብሎ ነው በኢኮኖሚ እድገት ክ10 እስክ 11 እጅ ለተከታታይ ዓመታት ውጤት አምጥቻለሁ የሚል መንግስት ከዓለማቀፍ ተራድኦ ህዝቡን ለማብላት እርጥባን ጠያቂ የሚሆነው?” እኒህ ማንም ጤናማ አእምሮ ያለው ሰው የሚጠይቃቸው ጥያቄዎች ናቸው። በተለይ የዜና ስርጭቱ ሁሉ በራብና ድርቁ ላይ ሲሆን። የኒህ ጥያቄዎች መልስ ከተራበውና ከተጠማው አርሶ አደር ስቃይ ይገኛል። ከወጣትዋ የአበባ ማምረቻ ሰራተኛ ይገኛል።ከመክረኛውም ህዝብ ሁሉ። ጭብጡ ሁኔታ ይህ “እድገት” ይህ “አምራችነት” የህዝብ ኑሮ ጨርሶ እያወደመ፤በጣም ተፈላጊ የሆነው ውሃ ለአበባ ማምረቻ ይውላል።ተፈጥሮም በመርዘኛ ጸረተባይ ዲ ዲ ቲ እና ሌላ መዳኒት ይበከላል።

የዛሬውን የቫላንታይን ቀን በትኩሱ በተቆረጡ አባቦች ስታከብሩ በግፍ ከኖሩበት ቀዬ የተፈናቀሉትን ገበሬዎች አስቧቸው። ወጣትዋን ብሩክን አስቧት።በመርዝ የሾቀ ቦታ ሰርታ የምትኖረውን አስቧት።ከሁሉም በላይ 10 ሚሊዮን ራብተኞችን ከዚህም 400000 ህጻናት ለጠኔ ተዳርገው ለም መሬታቸው እህል ሳይሆን አበባ የሚመረትበት መሆኑን እናስብ። እራሳችሁን ደግማችሁ ጠይቁ እንዴት አበባ ለአውሮፓ አቅራቢዋ አገር ራብተኛ ልትሆን ቻለች ብላችሁ።እንዲያው ምን ህሊና ይፈርዳል እንዲህ የመረተውን አበባን መግዛት ? ከበርቴ ትርፉን ሲል ሚሊዮኖች የለት ጉር ያጣሉ። ይህ ወንጀል ነው።ተባባሪም ደጋፊም አትሁኑ። ክዚህ ይልቅ ለኢኮኖሚም ለፖለቲካም ፍትህ የምትታገሉ ሁኑ።

ደራሲውን ለማግኘት

alem6711@gmail.com

3

The post የኢትዮጵያ የራብ ጽጌረዳዎች | ‘በሰው መከራ የተመረቱ አበቦች ከአውሮፓ ገበያ ይደርሳሉ’ በሚል ርእስ ከተጻፈ የእግሊዝኛው ጽሁፍ ትርጉም appeared first on Zehabesha Amharic.

ነገረ ‹ቀለም አብዮት›

$
0
0
በዘላለም ክብረት *
ሁለቱም ሃገራት በይፋ የዲፕሎማሲ ግንኙነት ከጀመሩ መቶ ዓመታት አልፈዋል፡፡ ሁለቱም በተመሳሳይ ወቅት ከኮሚኒስታዊ አስተዳደርና ስርዓት መፋታታቸውን ባወጁ ማግስት ዴሞክራሲን ተግባራዊ የማድረግ ፈተና አጋጥሟቸዋል፡፡ ሁለቱም ሃገራት በተመሳሳይ ወቅት ባፀደቁት ሕገ መንግስታቸው የምርጫ ዴሞክራሲን (electoral democracy) አውጀዋል፡፡ ነገር ግን ሁለቱም ሃገራት ዴሞክራሲያዊ ሕገ መንግስታቸውን ካፀደቁ ወዲህ ተቃዋሚዎቻቸው ስልጣን ሊይዙ አልቻሉም፤ የመያዝ እድላቸውም ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጠበበ መጥቷል፡፡ ሁለቱም ሃገራት በአሁኑ ወቅት የአንድ ፓርቲ የበላይነት በእጅጉ የጎላባቸው ሃገራት ናቸው፡፡ ሁለቱም ከምዕራቡ ዓለም ጋር (በተለይም በአለፉት 10 ዓመታት ውስጥ) በዴሞክራሲ ጉዳይ እየተጨቃጨቁ እና ምዕራቡን ዓለምም እያንጓጠጡ ቀጥለዋል፡፡ በአሁኑ ወቅት ሁለቱንም ሃገራት እየመሩ ያሉት መንግስታት ትልቁ ፍርሃታቸው አድርገው የሚያቀርቡትም በምዕራባዊያን የሚደገፍ በእነሱ ቋንቋ ‹የቀለም አብዮትን› ነው፡፡ የሁለቱም ሃገራት የጊዜው ገዥዎች ምዕራቡ ዓለም በሚያራምዱት ርዕዮተ ዓለም ምክንያት ከስልጣን እነሱን ለማውረድ ቀን ከሌሊት እንደሚሰራና ይሄንም እስከ መጨረሻው እንደሚፋለሙት ይገልፃሉ፡፡ የምዕራቡን ዓለም ጣልቃ ግብነት ለመከላከልም ሕጋዊና ፖለቲካዊ እርምጃዎችን መውሰድ መጀመራቸውን ገልፀው፤ ጠበቅ ያሉ የመንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች (መያድ) እና የፀረ-ሽብርተኝነት ሕጎችን በስራ ላይ ማዋላቸውንም በኩራት ይገልፃሉ፡፡ በተለይም የመያድ ሕጋቸው ‹የውጭ ሐይሎችን› ከፖለቲካዉ ምህዳር ለማራቅ ያደረጉት እንደሆነ ሁለቱም በኩራት ይገልፃሉ፡፡ ኢትዮጵያና ሩሲያ፡፡
ያለፉትን አስር ዓመታት ምስራቅ አውሮፓንና የካውካስስ አካባቢን የሚገልፀው የፖለቲካ መገለጫ ‹አብዮት› ነው፡፡ ከአብዮትም ‹የቀለም አብዮት›፡፡ የኢትዮጵያም የፖለቲካ ምህዳር በተመሳሳይ ጊዜ ባጋጠመው ትኩሳት ምክንያት ከዚህ የአብዮት ተረክ (narrative) ጋር በእጅጉ የሚጋራው ነገር አለ፡፡ አብዮተኞቹ በኬየቭ አደባባይ ሲቆሙና ሲቀመጡ፣ አብዮተኞቹ ቲብሊሲን ሲያጥለቀልቋት ኢሕአዴግ እዚህ ያነጥሳል፤ የአደባባዮቹን ጥበቃ ያጠናክራል፣ አይናቸው በአብዮት ቀልሟል የሚላቸውን ግለሰቦች ያስራል፣ እጅግ ሰፊ ፕሮፓጋንዳ ስለ ቀለም አብዮት አስከፊነት በመንግስቱ ሚዲያዎች ይለቀቃሉ፡፡
በሜይ 23፣ 2014 የቀለም አብዮትን ዋና አጀንዳው አድርጎ ከተካሔደው ሶስተኛው የሞስኮ የዓለማቀፍ ደህንነት ስብሰባ ላይ የሩሲያ ተቀዳሚ ምክትል የመከላከያ ሚኒስትር ጀኔራል ቫለሪ ጋሪስሚዮቭ ካቀረቡት መወያያ ላይ የተወሰደ

በሜይ 23፣ 2014 የቀለም አብዮትን ዋና አጀንዳው አድርጎ ከተካሔደው ሶስተኛው የሞስኮ የዓለማቀፍ ደህንነት ስብሰባ ላይ የሩሲያ ተቀዳሚ ምክትል የመከላከያ ሚኒስትር ጀኔራል ቫለሪ ጋሪስሚዮቭ ካቀረቡት መወያያ ላይ የተወሰደ

(የዩክሬን ሁለተኛው አብዮት በ2014 ሲከሰት በሚያዚያ ወር ውስጥ ብቻ ከታተሙት ሐያ ስድስት የአዲስ ዘመን ጋዜጣ እትሞች ውስጥ ‹ዩክሬንን ያየ በእሳት አይጫወትም›፣ ‹ዩክሬን ወደአደገኛ ሁኔታ በመሸጋገር ላይ ናት›፣ ‹ሩሲያ ዩክሬንን አስጠነቀቀች›፣ ‹አይሲሲ በዩክሬን ጉዳይ ምርመራ ሊጀምር ነው› የሚሉ ፅሁፎችን ጨምሮ በአስራ ሁለቱ እትሞች ለውጡን አጣጥሎ፤ ፑቲንን አጀግኗቸው እናገኛለን)
በእውነትም ያለፉትን አስር ዓመታት የኢትዮጵያን የፖለቲካ ምህዳር ‹የቀለም አብዮት› እንደሚለው ሃረግ የወረረው ፖለቲካዊ መለያ አለ ማለት ከባድ ነው፡፡ ኢሕአዴግ በየቀኑ የሚጨነቅለት/የሚጨነቅበት፣ ተቃዋሚው በቧልት የሚያየው፤ ነገር ግን ብዙዎቹን ዋጋ እያስከፈለ ያለ ተረክ – ‹የቀለም አብዮት›፡፡
የኢትዮጵያን ፖለቲካ የማቅለም ሒደት
የቀለም አብዮት የሕዝባዊ አመፅ ቅፅል ስም ነው፡፡ የምስራቅ አውሮፓን የድህረ-ምርጫ ሕዝባዊ አመፆች ተመሳሳይነት ለመግለፅ ልሂቃን ያዳበሩት ስያሜ ነው፡፡ እንደ ሩሲያ ባሉ ሐገራት ደግሞ ‹ሕዝባዊ አመፅ› የሚለው መጠሪያ ‹ሕዝባዊነት› ስላለው የቀለም አብዮት የሚለውን መጠሪያ መጠቀም ነገስታቱ ይወዳሉ፡፡ ስያሜው አዎንታዊና አሉታዊ ትርጉም በየሀገራቱ ይሰጠዋል፡፡ በአሁኗ ኢትዮጵያ ‹የቀለም አብዮት› እጅግ የተወገዘ እና ለከፍተኛ ቅጣት የሚዳርግ ሲሆን – በብዙ ሐገራት ግን የሕዝብ ፍላጎት የሚገለፅበት ኹነት ተደርጎ ይወሰዳል፡፡
ኢትዮጵያ ውስጥ ይህ ስያሜና ወቀሳ የተጀመረው በባለ ብዙ ታሪኩ ምርጫ ‘97 ወቅት ነው፡፡ ከምርጫ ’97 በፊት ገዥው ፓርቲ ብረት ያነሱትን ፋኖዎች ከሰላማዊ ታጋዮች ጋር በአንድ ላይ የሚጠራበት ስያሜ ነበረው ማለት አይቻልም፡፡ ‹ፀረ-ሰላም ሐይሎች› ከሚለው ብዙም የማይስብ ስያሜ ያለፈ ሕዝቡን የሚገዛ መጠሪያ ነበረው ማለትም አይቻልም ነበር፡፡ ገዥው ፓርቲ የቀለም አብዮት የሚለውን መጠሪያ አሉታዊ ትርጉም በመስጠት ነው መሰየሙን የሚጀምረው፡፡ ገዥው ፓርቲ በተመሳሳይ ወቅት ለቀለም አብዮት የሰጣቸውን ሁለት ትርጉሞች ማየት ምን ያክል አሉታዊነት እንደሚንፀባረቅበት ያሳያልና እንመልከታቸው፡፡

የቀለም አብዮት በውክልና ወይም በሶስተኛ አካል ፍላጎት በጎዳና ላይ ነውጥ በሕዝብ ድምጽ ስልጣን የያዙ መንግስታትን ከስልጣን የማውረድ ሙከራ ወይም ሴራ ነው፡፡ […] [በሌላ አነጋገር] በውክልና ወይም በሶስተኛ አካል ፍላጎት ላይ ተመስርቶ የሚካሔድ መፈንቅለ መንግስት [ነው] […]፡፡

አዲስ ዘመን፡ ዘወርዋራው የቀለም አብዮት መንገድ፣ ሚያዚያ 2006

የቀለም አብዮቶች ሁሉ የሚመሩት በአድህሮት ዓለማቀፍ ሃይላት ራሳቸውን ብሔራዊ ጥቅም በሌሎች ሀገራት ላይ ለማስጠበቅ ምሁራንን እና የግሉን ፕሬስ በቅጥረኝነት በመግዛት የሚቀሰቅሱት አመፅና ሁከት ደም መፋሰስ ሲሆን አብዮት ተብሎ ሊጠራ የማይችል ጸረ ህዝብና ፀረ ሀገር [እንዲሁም] ፀረ አብዮት ክንውን ነው፡፡

አዲስ ዘመን፡ አለን ለማለት አጉል መታከት፣ ሚያዚያ 2006
በረከት ስምኦን ‹የሁለት ምርጫዎች ወግ› ባሉት የ1997 እና የ2002ን ምርጫ ባነፃፀሩበት በፅሃፋቸው ‹የሰላማዊ ትግል ማኪቬሊ› (The Machiavelli of non-violence) እየተባሉ የሚጠሩት ጅን ሻርፕ በጎርጎሮሳዊያኑ አቆጣጠር የበርማን ሰላማዊ ትግል ለመርዳት የፃፉት ‹FromDictatorship to Democracy› የተባለ መፅሃፋቸው ወደ አማርኛ ‹ከአምባገነናዊ አገዛዝ ወደ ዴሞክራሲ› ተብሎ ተተርጎሞ ገበያ ላይ ስናገኝው ተቃዋሚዎችና የውጭ ሐይሎች ምርጫ ‘97ን ለማደናቀፍ በማሰብ የቀለም አብዮት እንደወጠኑ ደረስንበት ይላሉ፡፡ ይህን የሚሉን በ2003 ሲሆን ወደኋላ መለስ ብለን በ1997 ገዥው ፓርቲ የወሰዳቸውን አንዳንድ ርምጃዎች ስንመለከትም አንዳንድ እውነታዎችን ማግኝት እንችላለን፡፡
ገዥው ፓርቲ በምርጫው ወቅት ተቃዋሚዎች ‹በፍኖተ ነገደ› እየተመሩ ምርጫውን ሊያውኩ እየተዘጋጁ ነው በማለት ዶር ነገደ ጎበዜ በ1996 መጨረሻ ያሳተሙትን ‹ሕገ መንግስት ምርጫና ዴሞክራሲ በኢትጵያ፡ ከትላንት ወዲያ እስከ ነገ› የተባለ መፅሃፍ ‹የቦይኮት› ምክር እያጣቀሰ በምርጫው የመጀመሪያ ወራት ይፅፍ ይናገር ነበር፡፡ ተቃዋሚዎችም ምርጫውን ‹ቦይኮት› አላደረጉም፤ የገዥው ፓርቲም ትንቢት አልሰራም በዚህ በኩል፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ የካቲት 22/1997 ምርጫውን ለመታዘብ ከአሜሪካ ከመጡ ድርጅቶች መካከል ሶስቱን ማለትም የአሜሪካው ዴሞክራቲክ ፓርቲ የውጭ ክንፍ የሆነውን እና በቀድሞዋ የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር የሚመራውን National Democratic Institute (NDI)፣ የአሜሪካው የሪፐብሊካን ፓርቲ የውጭ ክንፍ የሆነውንና በ2001 የአሜሪካ ምርጫ የሪፐብሊካን ፓርቲን ወክለው ከባራክ ኦባማ ጋር በተወዳደሩት ሴናተር ጆን ማኬን የሚመራውን International Republican Institute (IRI) እንዲሁም International Foundation for Electoral System (IFES) ከሀገር በማባረር የወሰደው ርምጃ የቀጣዮቹን አስር ዓመታት ኢሕአዴጋዊ የፖለቲካ ተረክ ግልፅ ያደርገዋል፡፡
በወቅቱ በርምጃው የተበሳጩት ማዳም ኦልብራይትና ሴናተር ማኬን ለቀድሞው ጠ/ሚ በፃፉት ደብዳቤ በድርጅቶቹ ከ20 ዓመታት በላይ ባስቆጠረ ስራ ከአንድ ሀገር ሲባረሩ ይህ የመጀመሪያቸው እንደሆነና ውሳኔውም የምርጫውን ሒደት በእጅጉ እንደሚያጠለሸው ገልፀው፤ ድርጅቶቹም በዋናነት የሚረዱት በUSAID እንደሆነም አመልክተው ውሳኔው እንዲቀየር ጠይቀው የነበረ ቢሆንም ገዥው ፓርቲ እነዚህን ድርጅቶች ያለፈቃድ ነው ወደሃገር የገቡት በሚል ሰበብ ክልከላውን አፅንቷል፡፡ ነገር ግን በጊዜው የተሰጠው ያለፈቃድ ነው የገቡት የሚለው ምክንያት እየቆየ በሔደ ቁጥር ሌላ ምክንያት ያለው መሆኑ መገለፁ አልቀረም፡፡ ይሄም የሆነው ምርጫውን ተከትሎ ገዥው ፓርቲ እስከ 2002 ምርጫ ድረስ ባለው ጊዜ ውስጥ አጠናክሮ የጀመረው የቀለም አብዮት ውርጅብኝ ነው፡፡ በዚህ ጊዜ ውስጥ ከላይ የተጠቀሱት ሶስት ድርጅቶች የቀለም አብዮትን ዓለም ላይ ለማስፋፋት ቀንደኞቹ እንደሆኑ ግልፅ አድርጓል፡፡ ዛሬ ኢሕአዴግ ለአባላቱ በሚያሰራጫቸው ማንኛውም አይነት ፕሮፓጋንዳም ሆነ በመንግስታዊ ሚዲያዎቹ በሚያሰራጫቸው ከቀለም አብዮት ጋር በተያያዙ ፕሮግራሞች እነዚህን ሶስት ድርጅቶች ሳይጠቀሱ ማግኝት ከባድ ነው፡፡
ገዥው ፓርቲ የቀለም አብዮት ተረክን በእግሩ ካቆመው በኋላ ለዚህ ተረክ መከራከሪያ ይሆነው ዘንድ በቀለም አብዮት ላይ ያለውን አቋም የሚገልፅና ሕልዮታዊ መሰረት (theoretical background) ለማስያዝ በ2002 ምርጫ መዳረሻ ላይ የድርጅቱ የርዕዮተ ዓለም መፅሄት እንደሆነች በተነገረችው ‹አዲስ ራዕይ› መፅሄት ላይ ‹የቀለም አብዮትና አራተኛው አገራዊ ምርጫ በሚል ርዕስ አንድ ፅሁፍ በማቅረብ በወቅቱ በሚሊዮኖች ለሚቆጠሩት አባላቱ እንዲወያዩበት ትዕዛዝ አውርዶ ነበር፡፡ የፅሁፉ ፀሃፊ መፅሄቱ ላይ ባይጠቀስም ሚያዚያ 11/2006 የወጣው አዲስ ዘመን ጋዜጣ ‘‹የቀለም አብዮት› ለማንም የማይበጅ የጥፋት መንገድ’ ባለው ርዕሰ አንቀፁ ከዚህ ፅሁፍ ላይ በሰፊው ጠቅሶ በስህተት ይሁን በድፍረት ፅሁፉን የፃፉት የቀድሞው ጠ/ሚ መለስ ዜናዊ ናቸው ይለናል፡፡
ከዚህ ጊዜ በኋላ የቀለም አብዮት በእያንዳንዱ የገዥው ፓርቲ የፕሮፓጋንዳ ፅሁፍ ስር የማይጠፋ አያጅቦ (bogyman) ነው፡፡ ከ2003 አጋማሽ ጀምሮ በሰሜን አፍሪካና በመካከለኛው ምስራቅ በተነሳው ሕዝባዊ ቁጣ ምክንያት አምባገነኖች ከስልጣናቸው ሲገረሰሱ ኢሕአዴግ የቀለም አብዮት እየታሰበብኝ ነው ብሎ ካድሬዎቹን በንቃት እንዲከታተሉ ጠቁሞ መስከረም 2004 እነእስክንድር ነጋን ‹የቀለም አብዮት አስባችኋል› በማለት አስሮ ያልሞቀውን ለማብረድ ሞክሯል፡፡ በ2004 ታሕሳስ አደባባይ የወጣውን የኢትዮጵያ ሙስሊሞች የመብት ጥያቄም ለማፈን ይሄን የቀለም አብዮት ካርድ መምዘዙ አልቀረም፡፡ ለዚህ ጥሩ ማሳያ የሚሆነው በሚያዚያ 2006 ‹አክራሪነትን ለመዋጋት ዳግም የተገባ ቃል› በሚል ርዕስ በመንግስታዊው አዲስ ዘመን ጋዜጣ ላይ በወጣ ፅሁፍ፡

ሌላው ኢትዮጵያ ውስጥ አክራሪነትና ሽብርተኝነት ለማስፋፋት የተካሔደው ሙከራ ዶ/ር ጃሲም ሱልጣን በተባሉና እ.ኤ.አ በ1999 ዓ/ም የከሰመው የኳታር ሙስሊም ወንድማማቾች ፓርቲ አባል በነበሩት ግለሰብ በኩል የተከናወነ ነው፡፡ እኒህ ግለሰብ በሙስሊም ብራዘርሁድ ፓርቲ የአክራሪነት አስተምህሮ የተቃኘ የቀለም አብዮትን ለማካሄድ የሚያስችሉ ስልጠናዎችን በመስጠት ይታወቃሉ፡፡ የዶ/ር ጃሲም አስተምህሮ ወደ ኢትዮጵያ የዘለቀው በካሚል ሸምሱና አህመድ ሙስጠፋ በተባሉ ሁለት ግለሰቦች ነው፡፡

በማለት የሙስሊሙ የመፍትሔ አፈላላጊ ኮሚቴ አባል የሆኑትን ሁለት ግለሰቦች በመጥቀስ … በሙስሊም ብራዘርሁድ ፓርቲ የአክራሪነት አስተምህሮ የተቃኘ የቀለም አብዮትን ለማካሄድ … በሚል ውንጀላ ንቅናቄውን የቀለም አብዮት ያደርገዋል፡፡
በ2006 መጨረሻ በኦሮሚያ ክልል የተከሰተውን ተቃውሞ ተከትሎ ደግሞ ገዥው ፓርቲ አሁንም ጣቱን የቀለም አብዮተኞች ወዳላቸው ግለሰቦች/ፓርቲዎች መጠቆሙን አልተወም፡፡ ‹በአዲስ አበባ – ኦሮሚያ ሽፋን ስንኩል የሽብር ሴራ› በሚል ርዕስ ሚያዚያ 27/2006 መንግስታዊው አዲስ ዘመን ጋዜጣ ላይ በወጣ ፅሁፍ፡

በፖለቲካ ፓርቲ ስም ተደራጅተው በሕግና ሕጋዊ አግባብ መወዳደርም መመረጥም ሲያቅታቸው በቀለም አብዮት ስልጣንን መንጠቅ ሁሌም የሚከጅላቸው ኃይሎች የጥፋት ልሳኖቻቸው ከሆኑ አንዳንድ የስም ጋዜጦች ጋር በፈጠሩት ያልሰመረ ጋብቻ በዩንቨርስቲዎቻችን የታየው ግርግር እንዲወለድ ሆኗል፡፡

ሲለን፤ እንዲሁም በዚሁ ጋዜጣ ላይ በግንቦት 2006 ‹ከሁለት ፅንፈኞች ሴራ አገራችንን እንጠብቅ› በሚል ርዕስ በወጣ ፅሁፍ ላይ፡

እንዲሁም ከኦሮሞዎች ፈቃድና ፍላጎት ውጭ ኦሮሚያን ገንጥለው ሕዝቡ ላይ እንዳሻቸው ለመፈንጨት የቋመጡና በቀለም አብዮት ስልጣን ለመንጠቅ የተመኙ የኦሮሞ ፓርቲዎች [ናቸው ሕዝቡን ወደ አመፅ የከተቱት]

በማለት ተቃውሞው የቀለም አብዮተኞች ሴራ እንደሆነ በመግለፅ ሁሉንም ተቃውሞዎች የቀለም አብዮተኞች ሴራ እንደሆኑ መበየኑን ቀጥሎበታል፡፡ ምርጫ 2007 ከመደረጉ ስድስት ወራት ቀደም ብለው ጠ/ሚ ኃይለማርያም ደሳለኝ ‹ተቃዋሚዎችና ኒዮ ሊብራል ሐይሎች ብሄራዊውን ምርጫ የቀለም አብዮት ለመቀስቀስ እየተጠቀሙበት ነው› በማለት ማስጠንቀቂያ ሰጥተው ነበር፡፡ምርጫው በተቃረበም ወቅት በምርጫ 2007 ‹የቀለም አብዮት ምልክቶች በቅድመ ምርጫው ታይተዋልን?› በማለት የሚጠይቀው ኢሕአዴግ ‹አዎ እየታዩ ነው› በማለት ራሱ ጠይቆ ራሱ ሲመልስ ነበር፡፡ በአሁኑ ወቅት በኦሮሚያ ክልል ያለውን ተቃውሞ ገና ከጅምሩ ሽብርተኞች የወጠኑት የቀለም አብዮት ሴራ መሆኑን ኢሕአዴግ በተደጋጋሚ ገልጻል፤ እየገለፀም ነው፡፡ በጉዳዩ ላይ አወያየዋቸው የሚላቸውን አካላትም ነገሩ ቀለም አብዮት እንደሆነ ሲሰብክ ከርሟል፡፡
በአጠቃላይ በአለፉት አስር ዓመታት የተካሔዱትን ሶስት ምርጫዎች ‹የቀለም አብዮተኞች ሊበጠብጡብኝ ሞክረዋል› በማለት የሚከሰው ገዥው ፓርቲ፤ በአስር ዓመቱ ውስጥ የተፈጠሩትን ሁሉንም ታላላቅ ሕዝባዊ ተቃውሞዎች (የአረቡ ዓለምን ሕዝባዊ ተቃውሞ ተከትሎ የነበረውን መነቃቃት፣ ከታህሳስ 2004 ጀምሮ እየተካሔደ ያለውን የኢትዮጵያ ሙስሊሞች እንቅስቃሴ እንዲሁም ከሚያዚያ 2006 ጀምሮ በኦሮሚያ ክልል እየተካሔደ ያለውን ሕዝባዊ ተቃውሞ) የቀለም አብዮተኞች እኩይ ሴራ ውጤት መሆኑን እየበየነ ቀጥሏል፡፡
‹የቀለም አብዮቱ› የውጭ ክንፍ
ገዥው ፓርቲ ሁሉንም አይነት ተቃውሞዎች የቀለም አብዮት ብሎ መፈረጁ ከፕሮፓጋንዳ አኳያ ትርፋማ ያደረገው ይመስላል፡፡ በአንድ ድንጋይ የሃገር ውስጡን ተቃዋሚዎች እንዲሁም በሌላ በኩል የምዕራብ ተችዎቹን ለመምታት ይጠቀምበታልና፡፡ ‹የቀለም አብዮት የምዕራቡ ዓለም የጣልቃ ገብነት ሙከራ ነው› በማለት መሰረቱን ማስቀመጥ የሚጀምረው ኢሕአዴግ ‹ይሄን ሐይል ከፖለቲካው ውጭ ማድረግ አለብኝ በማለት ነው› ዛቻና ዘመቻውን የሚጀምረው፡፡ ለዚህም ሲባል ከመንግስታዊው ቀጥተኛ ግንኙነት ባለፈ በራሳቸው መንገድ የምዕራቡን ዓለም መንግስታትም ሆነ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶችን የተገናኙ ግለሰቦች/ድርጅቶች ያለምንም ቅድመ ሁኔታ በኢሕአዴግ መነፅር የቀለም አብዮተኞች ቅጥረኞች ናቸው፡፡ ቅጥረኞች ያላቸውንም ግለሰቦች/ድርጅቶች ለምዕራብ ተላላኪዎቻቸው ሚታዘዙና ቀለብ የሚሰፈርላቸው ናቸው እያለ ‹ተለመደና ዘኬ ባልጫ ፤ ወደ መምሬ ቤት ሁልጊዜ ሩጫ› ሲል ይታያል፡፡
ለመሆኑ ገዥው ፓርቲ ‹የገበያ አክራሪነትን ለመጫን በመፈለግ ሩጥ ሲሉት የሚሮጥ፣ ዝለል ሲሉት ምን ያህል ልዝለል የሚል መንግስት በቀለም አብዮት ሊመሰርቱ ይፈልጋሉ› የሚላቸው የምዕራብ ሐይሎች እነማን ናቸው?
ይሔን መመለስ በጣም ከባድ ነው፡፡ ከባድ የሚሆነው ግን እነዚህን ሐይሎች ማወቅ ስለማንችል አይደለም፡፡ ይልቁንም እጅግ ብዙ ከመሆናቸው የተነሳ ዘርዝረን መጨረስ የማንችላቸው በመሆናቸው ነው፡፡ ገዥው ፓርቲ የቀለም አብዮት አቀጣጣዮች የሚላቸውን ድርጅቶች በትንሹ ማየቱ ጉዳዩን የበለጠ ግልፅ ስለሚያደርገው ቃል በቃል እንጥቀሳቸው፡

የቀለም አብዮቶች በሚነሱበት ሀገራት ሁሉ ከጀርባ መሪዎቹና አስተባባሪዎቹ ምዕራባዊያን መንግስታትና የእነርሱን ዓላማ አስፈፃሚ የሆኑት ዓለማቀፍ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ናቸው፡፡ (አዲስ ዘመን፡ በአረንጓዴው አብዮት የሚሰበረው የቀለም አብዮት፣ ሚያዚያ 2006) የቀለም አብዮት ዋነኛ አራማጁ ፋይናንሻል ታይምስ [ሲሆን]፣ የምዕራባዊያኑ የገበያ አክራሪ ኃይሎችን ቀለም አብዮተኖች መፈልፈያ የሆነው [ደግሞ] ኦክስፎርድ ዩንቨርስቲ [ነው]፡፡ (አዲስ ዘመን፡ የቀለም አብዮት ናፋቂዎች፣ ሚያዚያ 10፣ 2006) የዓለም አቀፍ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ጠቅላይና የቀለም አብዮት ዋነኛ ዘዋሪ የሆነው ናሽናል ኢንዶውመንት ፎር ዴሞክራሲ [ነው]፡፡ [ይህ] ድርጅ[ት] የመሪነቱን ድርሻ እንዲወጣም ዋነኛው የአሜሪካ መንግስት ፋውንዴሽን ሆኖ በስሩ በርካታ ዓለም አቀፍ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶችን በማቀፍ እንቅስቃሴ ጀመረ፡፡ ከእነዚህ አበይት አለም አቀፍ መያዶች መካከል ናሽናል ዴሞክራቲክ ኢንስቲትዮት ፎር ኢንተርናሽናል አፌይርስ፣ ኢንተርናሽናል ሪፐብሊካን ኢንስቲትዮት፣ ኢንተርናሽናል ፋውንዴሽን ፎር ኤሌክቶሪያል ሲስተም (እነዚህ ሶስቱ በምርጫ 97 ወቅት ምርጫውን እንዳይታዘቡ ከኢትዮጵያ የተባረሩት እንደሆኑ ከላይ አይተናል)፣ ኢንተርናሽናል ሪሰርች ኤንድ ኤክስቼንጅስ ቦርድና ፍሪደም ሃውስ የተሰኙ ተቋማት ይገኙበታል፡፡ ናሽናል ኢንዶውመንት ፎር ዴሞክራሲ የተደራጀው በቀድሞ የሲአይኤ አመራርና አባላት ከመሆኑም በተጨማሪ፤ ሌላኛው የሲአይኤ ገጽታ ነው ማለት ይቻላል (አዲስ ዘመን፡ የቀለም አብዮት መፍጠሪያ “ማሽኖች” እና ተላላኪዎቻቸው፣ መጋቢት 2006)፡፡ የዲሞክራሲ (sic) ጭንብል ካጠለቁ ዓለም አቀፍ የገበያ አክራሪነት አስፈጻሚ ተቋማት [እና የቀለም አብዮት አቀጣጣዮች] ውስጥ […] ዓለም አቀፍ የልማት ድርጅት በአሜሪካ (USAID) […] እንዲሁም በትውልድ አይሁዳዊ የሆነው ቢሊየነር ጆርጅ ሶሮስ […] [የሚመራው] ግልጽ የማሕበረሰብ ተቋም (the open socity (sic) institute) ይገኙበታል፡፡ ትርምሱን በስተጀርባ [ከ]ሚቀምሩት [መካከል] ደግሞ የአውሮፓ ሕብረት እና […] ‘የሰሜን አትላንቲክ የጋራ ጦር ቃልኪዳን ድርጅት (NATO) ይገኙበታል። (በይናገር ታሪኩ፡ ከቀለም አብዮት በስተጀርባ (behind the color revolution) የተደበቁ ቁማርተኞች (ለኢሕአዴግ አባላት ለውይይት የቀረበ ፅሁፍ) 2006)፡፡ [በዩክሬን ከተካሔደው ሁለተኛው የቀለም አብዮት በኋላ] የቀለም አብዮቱ አቀጣጣዮች ቡድን በፕሬዝደንቱ በኩል (የአውሮፓ ሕብረት ፕሬዝደንት) ዩክሬንን አወገዘ፡፡ በሐገራችንም ምርጫ 97 ወቅት የነበረው የአውሮፓ ህብረት ታዛቢ ቡድን አሁን ድረስ በሃይማኖት ስም አክራሪ ሃይሎችን እያሰረገና ፅንፈኛ ፖለቲከኞችንም እያንቀሳቀሰ መሆኑ ይታወቃል (አዲስ ዘመን፡ ዩክሬንን ያየ በእሳት አይጫወትም፣ ሚያዚያ 03፣ 2006)፡፡ [በሐገራችን ሊካሔድ የታሰበውን ምርጫ 2002ን ወደ ቀለም አብዮትነት ለመቀየር በማሰብ ሰሞኑን] ሒዉማን ራይትስ ዎች፣ የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት፣ አምነስቲ ኢንተርናሽናል፣ ኢንተርናሽናል ክራይስስ ግሩፕ… ከየጠቅላይ መምሪያቸው ተመሳሳይ ውንጀላ በማሰማት […] ለወጠኑት የቀለም አብዮት በመሳሪያነት የሚያገለግል እንዲሆን [ተንቀሳቅሰዋል]፡፡ ቢቢሲ፣ አልጀዚራ፣ ፕሬስ ቲቪ፣ ቪኦኤ የመሳሰሉት የውጭ ሚዲያዎች[ም] በግንባር ቀደም የቀለም አብዮት አራጋቢነት ተሰ[ልፈዋል] (አዲስ ራዕይ፡ የቀለም አብዮትና አራተኛው አገራዊ ምርጫ፣ መጋቢት – ሚያዚያ 2002)፡፡ [እንዲሁም] ዘጋርዲያን፣ ዋሽንግተን ፖስት፣ ኒው ዮርክ ታይምስ [ለቀለም አብዮት የተሰለፉ ሐይሎች እንደሆኑ ይታወቃል] (አዲስ ዘመን፡ ዘወርዋራው ቀለም አብዮት መንገድ፣ ሚያዚያ 2006)፡፡ [ከዚህም በተጨማሪ] […] እነ አርቲክል 19 የ2007ን ምርጫ ተከትሎ ለቀለም አብዮት መደላድል ለመፍጠር […] [ሙከራ እያደረጉ ሲሆን፤] እንደሚታወቀው አርቲክል 19 እና መሰል አክራሪ ኒዮ-ሊበራል ሃይሎች የሀገራችንን ሁለንተናዊ ዕድገት የኋሊት ለመቀልበስ ያልሞከሩት ሴራ የለም። ከሪፖርት ጋጋታ እስከ የቀለም አብዩት ጋሻ ጃግሬዎችን እስከ መመልመል ድረስ ተፍጨርጭረዋል፤ ምናባዊና ተግባራዊ ዳገት ወጥተዋል፤ ቁልቁለት ወርደዋል። (አዲስ ዘመን፡ “አርቲክል 19”— የመብት ተሟጋች ወይስ የቀለም አብዮት አዝማች? ግንቦት፣2006) …

እያልን መቀጠል እንችላለን፡፡ ዝርዝሩ አያልቅም፡፡ ገዥው ፓርቲ እነ ሲፒጄ፤ ኦክላንድ ኢንስቲቲዩት እና አልበርት አንስታይን ኢንቲቲውትን ጭምር ዋነኛ የቀለም አብዮት አቀጣጣይ ብሏቸው እናገኛቸዋለን፡፡ ከበርቴው ጆርጅ ሶሮስን ‹የቀለም አብዮት አባት›፣ ሶሻሊስቷን ወ/ሮ አና ጎሜዝን ደግሞ ‹የቀለም አብዮት እናት› ብሎ ማዕረግ ሰጥቷቸዋል፡፡ ስያሜው አያልቅም፡፡
ኢሕአዴግ የሚመራት ኢትዮጵያ በዓመት ከሚሰፈርላት አጠቃላይ እርዳታ አስር በመቶ ያህሉን የሚሸፍነው የአውሮፓ ሕብረት የቀለም አብዮት አቀጣጣይ ከተባለ፤ ከአመታዊ እርዳታዉ በUSAID በኩል እስከ አርባ በመቶ የሚሆነውን የምትሸፍነው አሜሪካ እንዲሁም በUSAID በጀት የሚተዳደሩት እነNational Endowment for Democracy (የNED እርዳታ ለአፍቃሬ ኢሕአዴጎችም እንደሚሰጥ ልብ ይሏል) የቀለም አብዮት አቀጣጣዮች ከተባሉ፣ በNATO የተለያዩ ወታደራዊ ርዳታዎች የምታገኝው ኢትዮጵያ NATOን የቀለም አብዮቱ አስተባባሪ ካለችው፣ አርቲክል 19 የገንዘብና የሙያ ድጋፍ በተለያዩ ጊዜያት ስታገኝ የነበረችው ኢትዮጵያ ዛሬ አርቲክል 19ን ዋነኛ የቀለም አብዮት አቀጣጣይ ብላ ከፈረጀችው፣ ሶሻሊስቷ አና ጎሜዝ ከከበርቴው ጆርጅ ሶሮስ እኩል የቀለም አብዮት አንኳር ከተባሉ… ማን ቀረ? በአሁኑ ወቅት ምንም እንኳን ለረሃቡም ሆነ ለችግሩ የሚደርሱት እነሱ ቢሆኑም፤ ገዥው ፓርቲ የቀለም አብዮተኛ ብሎ ያልሰየመው የምዕራብ አውሮፓ ድርጅትና መንግስት ማግኝት በጣም ከባድ ነው፡፡ ይህ ሲገርመን የመንግስታቱ ዝምታ ደግሞ የበለጠ እንድንደነግጥ ያደርገናል፡፡
‹የቀለም አብዮቱ› የሀገር ውስጥ ክንፍ
ከላይ ለመጥቀስ እንደተሞከረው ገዥው ፓርቲ ‹የቀለም አብዮት› በሚለው ስያሜ የሚተቹትን የውጭ መንግስታት እንደ ቀጣሪ፤ በሀገር ውስጥ ያለውን ማንኛውንም አይነት ተቃውሞ እንደተቀጣሪና ተላላኪ በመፈረጅ ሁለቱንም ወደጎን ለማድረግ ረድቶታል፡፡ በሀገር ውስጥ ያለውን ተቃውሞ አንዳንዴ ሕጋዊ ተቃዋሚዎችና ሕገ ወጡን ከሕጋዊው መንገድ ለመቀላቀል የሚሞክሩ ተቃዋሚዎች ከሚለው ክፍፍል ባለፈ በአብዛኛው ሁሉንም ተቃውሞና የሐሳብ ልዩነት የሀገር ውስጥ ሕዝባዊ መሰረት የሌለው፣ የውጭ ሐይሎች ቅጥረኛ እና የሀገር ክህደት (ባንዳዊ) ርምጃ እንደሆኑ ይገልፃል፡፡ እኔ አባል የሆንኩበት ዞን ዘጠኝ ከጓኞቻችን ጋር በመጀመሪያ ‹የቀለም አብዮት ለማቀጣጠል ሲሞክሩ ነበር› ተብለን በታሰርንበት ወቅት ገዥው ፓርቲ እኛን የሳለበት በመንገድ ለዚህ ጥሩ አብነት ነው፡

ሰሞኑን በድረ ገፆች ላይ በመስራት ለረጅም ጊዜ ዘመቻ ሲያካሂዱ፣ የአገሪቱን እና የመንግስትን ገፅታ ጥላሸት ሲቀቡ የነበሩት [የዞን ዘጠኝ] ግለሰቦች፣ የእርስ በርስ ግጭትና ጦርነት እንዲነሳ፣ የጎሳ ጦርነት እንዲቀሰቀስ፣ አገሪቱ ወደ ብጥብጥና ቀውስ ውስጥ እንድትገባ፣ የተጀመረው ልማት እንዲደናቀፍ፣ በዚህም የውጭ ኃይሎችን የግብፅ፣ የሻዕቢያና እንዲሁም የኒዮ ሊብራል ኃይሎችን አጀንዳ ለማሳካት ብዙ ዓመታት ሲሰሩ የነበሩ ቢሆንም በቁጥጥር ስር ውለዋል፡፡ […] የኢትዮጵያን ሕዝብ ብሔራዊ ሠላም ክብርና ጥቅም አሳልፈው ለውጭ ኃይሎች በመስጠት በቅጥረኝነት የተሰለፉት እነዚህ ወገኖች ድርጊታቸው በታሪክም ተጠያቂ ያደርጋቸዋል፡፡ ይልቁንም ለጠላቶቿ ታላቅ ፈንጠዝያ ለመፍጠር ሲሉ ተገዝተው የተሰለፉበት የጥፋት ጎዳና ለእነሱም ሆነ ለማንም አይበጅም፡፡

አዲስ ዘመን፡ ኢትዮጵያ በአመፅ አትፈርስም፣ ግንቦት 10፣ 2006

ሁኔታውን [የዞን ዘጠኞችን ድርጊት] እንደ ዜጋ ስንመለከተው አሳፋሪው ነገር፣ ትናንት “አዲስ አበባን እንደ ባግዳድ እናደርጋታለን” ያለውንና ይህ ቀቢፀ-ተስፋው እንደ ጉም ብን ብሎ የጠፋውን የሻዕቢያን ህልም ለማሳካት እንዲሁም የኢትዮጵያ ህዝብ የዘመናት ቁጭት የሆነውን፣ የ‘አይቻልም’ን መንፈስ የሰበረውንና እንደ ዓይኑ ብሌን የሚመለከተውን ታላቁን የህዳሴ ግድብ በሁከት እንዲቋረጥ ባንዳ ሆኖ መሰለፍ ነው። አባቴ ይሙት! ማንኛውም ዜጋ በእነርሱ [በዞን ዘጠኞች] ቦታ ሆኖ ማፈሩ አይቀርም። ባንዳነት ሀገራችን ውስጥ ‘ወንዜነት’ የሌለው ሀገርን አሳልፎ የመስጠት አሳፋሪ እሳቤ ነውና።

አዲስ ዘመን፡ የ“ዞን 9 አባሎች”—ጦማሪዎች ወይስ ህቡዕ ተቀጣሪዎች?፣ ሰኔ 2006
በነዚህና በመሳሰሉት ፍረጃዎች ተቀጣሪ የሚላቸውን ሐይሎች ባንዳና እና አቆርቋቋዥ በሚል ስያሜ በህብረተሰቡ ውስጥ እንዲጠሉና ራሱን የሀገሪቱ ችግሮች መድኃኒት አድርጎ ያቀርባል፡፡ ይህ ከነሱ አስተሳሰብ ውጭ የሉትን ዜጎች ብሄራዊ ስሜት የሌላቸውና ባንዳ እንደሆኑ አድርጎ ማቅረብ ያረጀ አምባገነናዊ ስልት ሲሆን፤ በብዙ ሀገሮች ተቃውሞን ለማጣጣል ጥቅም ላይ ሲውል የነበረ አሁንም እየዋለ ያለ ነው፡፡
ሰርቢያዊው ስራዳ ፖፖቪች በጎርጎሮሳዊያኑ 2000 የአምባገነኑን ስሎቦዳን ሚሎሶቪችን ስርዓት በተማሪዎች ተቃውሞ ያስወገደው የOTPOR የተባለውን ቡድን ያደራጀና የመራ ሲሆን በቅርቡ በLegatum Institute ባቀረበው አንድ ፅሁፉ ላይ ያጋጠመውን ሲገልፅ:
‹‹ተቃውሟችንን ከጀመርን በኋላ በአንድ ሞቃት የበጋ ቀን ሶስት የመንግስት ሚኒስትሮች በቴሌቪዥን ቀርበው ‹በሲአይኤ የተቀነባበረና በቅጥረኛ ተማሪዎች እየተካሔደ ያለ እንቅስቃሴ ነው› ሲሉ ሰማሁ፡፡ ወዲያውም…›› ይላል ፖፖቪች ‹‹…የሴት ጓደኛዬ ደውላ እየሳቀች ‹የኔ የውጭ ቅጥረኛ፣ ወፍራም ቼክ እንደተቆረጠልህ እንዴት አላወኩም፤ ብሩማ ከመጣ ልታዝናናኝ ነው ማለት ነው?› አለችኝ እያሾፈች›› ይላል፡፡
(አዲስ ዘመን ጋዜጣ በሚያዚያ 28/2006 ባወጣው ‹ዘወርዋራው ቀለም አብዮት መንገድ› በተባለ ፅሁፍ ‹‹ኦትፖር የተባለው የሰርቢያ የአክቲቪስት ግሩፕ ለሚያደርገው የቀለም አብዮት በዩናይትድ ስቴትስ መሰረቱን ካደረገው አልበርት አንስታይን ኢንስቲቲውት የስትራቴጅ ስልጠናና የሕትመት [የገንዘብ] ልገሳ ይደረግለት እንደነበር ይታወቃል›› በማለት አስቂኙን ጉዳይ ይደግመዋል፡፡)
‹‹ይህ አይነት ተቃውሞ ሁሉ የውጭ ሐይሎች ሴራ ነው የሚል ተረክ ለአምባገነኖች ሁለት አይነት ጥቅሞችን ይሰጣል›› የሚለው ፖፖቪች ‹‹አንደኛ ተቃውሞዎችን እና የሐሳብ ልዩነቶች ሁሉ ከውጭ የሚጫኑ ናቸው ከተባለ ተቃዋሚዎች ሁሉ ባንዳዎች እና ሀገር የካዱ እንደሆኑ ለሕብረተሰቡ ይገልፃል፤ ሁለተኛ ሕብረተሰቡ አይኑን ወደ ውስጣዊ ችግሮች እንዳያዞር በማድረግ ሀሳቡን ሁሉ እነዚህ የውጭ ሐይሎች የተባሉት ላይ እንዲያደርግ ያስችላቸዋል›› በማለት ይገልፃል፡፡ ይህ የቀለም አብዮት የተባለ ተረክም ተመሳሳይ ውጤት ያለው ሕብረተሰቡን የማደንዘዣ (the Opium of the Mass) መሳሪያ ነው ማለት ይቻላል፡፡
‹‹በአንድ አገር ውስጥ የቀለም አብዮት እንዲኖርና አልፎ ተርፎም እንዲሳካ ከማድረግ አኳያ ከሌሎች ነገሮች በተጨማሪ ጠንካራ አንድነት ያለው የተቃዋሚ ጎራ መኖር እንዳለበት በመስኩ የተራቀቁት የቀለም አብዮተኞች ይገልፃሉ፡፡›› (አዲስ ራዕይ፡ የቀለም አብዮትና አራተኛው አገራዊ ምርጫ፣ መጋቢት – ሚያዚያ 2002) የሚለው ገዥው ፓርቲ ሀገሪቱን ያለምንም ተቀናቃኝ ተቆጣጠሯት እንኳን ከቀለም አብዮት ፕሮፓጋንዳው ፈቅ አለማለቱን ስናይ ፖፖቪች ባለው አንፃር ችግሮችን ሁሉ ከውጭ የመጡ አድርጎ የማቅረብ (externalization) አካሄድና ራሱ ግን ምሉዕ በኩልሔ እንደሆነ የማሳየት ዓላማ እንደሆነ ለመረዳት ብዙም አያዳግትም፡፡ ‹‹ኢትዮጵያ ለበጎ አድራጎት ድርጅቶች ያወጣችው አዋጅ እራሷን ከአክራሪ ዓለማቀፍ አክራሪ የገበያ ኃይል ለመከላከልና ከቀለም አብዮት ለመታደግ እንዲቻላት [ነው]፡፡›› (አዲስ ዘመን፡ የቀለም አብዮት ናፋቂዎች፣ ሚያዚያ 10፣ 2006) በማለት በግልፅ የሚናገረው ገዥው ፓርቲ ይህን ካደረገ ከሰባት ዓመታት በላይ ቢያልፈውም አሁንም ቀለም አብዮተኞች መጡብህ እያለ ቀጥሏል፡፡ የቀለም አብዮት የምዕራብ የገበያ አክራሪዎች ደባ ነው ሲል ቆይቶ ሲያሻው ደግሞ ‹…በሙስሊም ብራዘርሁድ ፓርቲ የአክራሪነት አስተምህሮ የተቃኝ የቀለም አብዮት…› እያለ አሁንም የህዝብን ተቃውሞ ሁሉ ማጣጣሉን ተያይዞታል፡፡
ገዥው ፓርቲ ተቃውሞዎችን ሁሉ ‹የውጭ ሐይሎች ደባ›፣ ተቃውመው አደባባይ የወጡትን ዜጎች ሁሉ ‹ቅጥረኞች› እያለ ለጥያቄዎቹም መልስ መስጠትን እምቢ ብሏል፤ ለጠያቂዎቹም ስብዕና እውቅና እንኳን መስጠት አልፈልግም ብሎ ቀጥሏል፡፡ ከላይ የጠቀስነው ፖፖቪች ‹ከእንደዚህ አይነት መንግስታት የሚመጡትን ‹የውጭ ሐይሎች ናቸው – የውጭ ቅጥረኞች ናችሁ› ውንጀላዎች እንደቁም ነገር መውሰድ የለብንም፤ ይልቁንም ለእንደዚህ አይነት ውንጀላዎች ትክክለኛው መልስ ቧልትና ቀልድ ነው› ይላል፡፡ በርግጥም ‹የችግሮቻችን ሁሉ ምንጮች አውሮፓና አሜሪካ ናቸው› በማለት ሀገሩን ሲያምስ ቆይቶ ሲቸግረው እጁን ወደ አውሮፓና አሜሪካ ለልመና የሚዘረጋ መንግስት ከቧልት የዘለለ መልስ አይገባውም፡፡
* (የዞን 9 አባሉ ዘላለም ክብረት ይህን ጽሁፍ በፌስቡክ ገጹ ያሰፈረው ነው)

The post ነገረ ‹ቀለም አብዮት› appeared first on Zehabesha Amharic.

መለከት ድራማ ክፍል 43

ኃይሌ ገብረሥላሴ የተቃርኖ – የስኬትና የውድቀት – ምልክት ሲሆን (በሀገሬ ክብሬ)

$
0
0

በሀገሬ ክብሬ

44በሀገራችን እርምጃው የሚያፈጥነው ሰው “እገረ ቀሊል” ይባላል። ይሄ የበርካታ ክብረወሰን ባለቤት ለሆነው የሩጫው ጀግና ኃይሌ ቢያንሰው እንጂ አይበዛበትም። ክፋቱ ግን እግዜሩ ሀይሌን ሲያድለውና ሲበድለው በእግሩ ሮጦ ለሚያገኘው ድል ሲከበርና ሲወደድ ከጭንቅላቱ የሚፈልቀው ሀሳብ አስተዋይነትና ጨዋነት ማጣቱ በኢትዮጵያና ዛሬ በአለም ህዝብ ፊት ቀላል ሰው አደረገው። “ቀሊል (ቀላል)” የሚለው አባባል ለእግሩም ለማሰብ አቅሙም መገለጫ መሆኑ ያሳዝናል።

ሀይሌ ስለህይወቱ ሲተርክ እንደሰማነው በልጅነቱ ያስሮጠው ምክንያት እንደ አብዛኛው ህዝባችን የሱም ቤተሰቦች የነበራቸው የነገን የማሰብ ሀብትና የነበረባቸው የገንዘብ ድህነት ነበር። አስተዋይ ባይሆኑ ትምህርትቤት አይልኩትም ነበር። የገንዘብ ደሀ ያባይሆኑ ደግሞ እንደየዛሬ ጓደኞቹ ዘራፊ ወያኔ ልጆች የግል አዳሪ ትምህርትቤት ይላክ ነበር ወይንም ሞግዚት ምሳና ደብተሩን ተሸክሞለት በሹፌር ከቤት ትምህርትቤት በተመላለሰ። ድህነት ረዳውና ያቺ ወደትምህርትቤት ሲሮጥ ደብተሩን ያቅፋበት የነበረችውን እጅ ቆልመም አድርጎ በመሮጥ ድህነትን እንደበቆሎ እሸት ገለባ ከላዩላይ ገሽልጦ በመጣል ተፈትልኮ አመለጣት። እሰየው የሚያስብል ነበር ይሄ ስኬቱ ጥጋብና ማናለብኝ ባይነት የአመለካከቱን ኋላቀርነት አደባባይ ለማውጣት ድፍረቱን ባያበዛበት።

ታድያ ይሀው ዛሬ በፊልም አስቀርጾ ያሳየን እኔም እንደተቀረው ወገኔ በችግርነው ያደኩት የሚለው ትረካ ተረሳና ሸገር ከፍ ያለ መሬት ላይ ቪላ ሰርቶ ከህዝብ የሚቀማ መሬት  ላይ ሀብት እያካበተ በህዝቡ መከራ እያላገጠ ቀን ይገፋል።  ይኖራል ማለቱ ይከብደኛል ምክንያቱም አጠገቡ በረሀብ የሚረፈረፈውና በፍትህ እጦት የሚሰቃየው ህዝብ መከራ የማይከነክነው ፍጡር “ኖረ” ማለት ቀርቶ ሰውም ነው ማለቱ ይከብዳል።

ችግሩ ኃይሌ መበልፀጉ አይደለም። እንኳን እሱ ብዙ ጊዜ ባንዲራችን በዓለም ላይ ከፍ ብሎ እንዲውለበለብ ያደረገና ለሀብቱ መነሻው የራሱ ጥረት የሆነ ኢትዮጵያዊ ቀርቶ ሀገራችንን ከማጥፋትና ባንዲራችንን ከማዋረድ የተለየ ነገር በህይወታቸው አንድም ቀን ሊያደርጉት ቀርቶ ሊያልሙትም የማይቻላቸው በርካታ የወያኔ ማፈሪያዎችስ በህዝባችን ጫንቃ ላይ በልፅገው የለ? ሀይሌ የግፉ ተባባሪና የግፈኞቹ ጠበቃ ለመሆን ከአፉ ቀደም ቀደም ማለትን አለቅጥ ማብዛቱ ነው የሚያሳዝነው።

“የማያድግ ልጅ ሽቀብ ይቀ..ል” እንደሚባለው ኃይሌ ዛሬ አፋፍ ላይ ካለው ቪላ ቤቱ መናፈሻ ውስጥ እየተንጎራደደና ህዝባችንን ቁልቁል እያየ “ስንጠግብ እጃችንን ጠረግ ጠረግ ያደርግንበትን የሼራተን ትርፍራፊ በጉርሻ መልክ እየገዛህ ረሀብህን ማስታገስ ከቻልክ መቼ አነሰህ? ዲሞክራሲስ ላንተ ምንህ ነው” እያለ በኢትዮጵያውያን ላይ ብቻ ሳይሆን በመላው አፍሪካውያን ላይ ማላገጥን እንደ አስተዋይነት ቆጠሮት ይህን ሰንካላ አስተሳሰብ (ማሰብ ከተባለ) አደባባይ ይዞት ወጣ። እንዴት ነው ጋዜጠኛው እንኳን ይታዘበኛል የማይለው? ከኛዋ ኢትዮጵያ እጅግ በጣም የተሻለ የዲሞክራሲ ስርዓት ያለበት ሀገር ያሉት ጓደኞቹስ ምን ይሉኛል እንኳን አይልም?

ኃይሌ ቀደም ሲል በ”ከማን አንሼ” አስተሳሰብ በዘመነ ወያኔ የደንቆሮ መፈንጫ የሆነችው ኢትዮጵያ መሪ መሆን እፈልጋለሁ እችላለሁም እንዳለው ነገ ለተባበሩት መንግስታት መሪም ልሁን ይል ይሆናል። እንዳለውም ከመቶ ሀገር በላይ መሂዱና ሮጦ መመለሱ አለምን አውቃለሁና ለአለም መሪነት የሚያበቃ እውቀትና ብቃትም ተጎናፅፈያለሁ ይልም ይሆናል። ሲያልቅ አያምር እንዲሉ።

የኃይሌ ባህሪይ እናቴ በልጅነት ዘመኔ የነገረችኝን ምሳሌ አስታወሰኝ። አንዱ አርሶአደር የሽምብራ ማሳው ውስጥ እንቅስቃሴ ያይና ዝንጀሮ መስሎት ለማባረር ሲሄድ አንዱ ሰውዬ የሽምብራ እሸቱን እየዘነጠለ ከነገለባው ሲቅም ያየዋል። አርሶአደሩም የተራበ ሰው አላስደንግጥም ብሎ በትዕግስት ከርቀት ማየቱን ቀጠለ። እንደዝንጀሮ የሰው ማሳ የወረረው ሰውዬም ረሀቡ ጋብ ሲልለት ሽምብራውን ከነውጪ ገለባው መቃሙን አቁሞ እየጠረጠር ከበላ በኋላ በመጨረሻ የእያንዳንዱን ሽንብራ ስስ ቆዳ ሳይቀር እየላጠ ማላመጡን ቀጠለ። በዚህ ያልተደሰተው ባለማሳውም ሰውዬውን ጠጋ ብሎት “እንደ መጀመሪያውም አይደል አንደመጨረሻው እንደመሀከለኛው ብላ” አለው። ሀይሌም እንደዱሮው የነጣ ድህነቱ ጊዜ ሳይሆን አንደዛሬም የሱ የቀድሞ ጎረቤቶችና ዘመዶች ሳይቀሩ መሬታቸውን እየተቀሙ ለስደትኝነት፣ ለለማኝነትና፣ እስር ሲዳረጉ ይህን አልሰማሁም አላየሁም ቢሆንስ ምናለበት አፍሪካ ነው ያለነው እያለ ማላግጡን አቁሞ በህዝብ ዘንድ ያለውን የተሟጠጠ ክብርና ፍቅር ጭራሹን ሳያጣ ሞቴንና ታሪኬን ያሳምረው ብሎ ህልፈት ህይወቱን ቢጠብቅ ይሻለዋል። እምብዛም ጥጋብና የህዝብ ንቀት ለመለስ ዜናዊም አልበጀው። ከህዝቡ የዘረፈውን በቢሊየን የሚቆጠር ብር ሳይበላው “አረመኔ ጨቋኝ” ተብሎ በአደባባይ በመዘለፉ ደንግጦ ሞቷል። ለመለስ ሞት አደባባይ የታየው የውሸት ለቅሶ ትዕይንት የፍቅር መገለጫ ነው ብሎ እራሱን ካላሞኘ ከአሁን ባህሪው ካልታረመ የሱም እጣፋንታ በሆዱ “እንኳን ወሰደው” በአፉ “ውይ ኃይልዬ ተቀጨ” የሚል ለቀስተኛ አስክሬኑን በፌዝ ለቅሶ አጅቦ እንደሚሸኘው አይዘንጋ።

ለሱም አደብ ግዛ የሚል መካሪ ይስጠው።  እኛም ከማሰብ አቅሙ በላይ እንዲያስብ እየጠበቅን የብቃቱን ውስኑነት ባሳየን ቁጥር መበሳጨቱ ይብቃን። ፈረንጅኛውን እንደተማረው የሰውልጅ በዳቦ ብቻ አይኖርም የሚልውንም ሀሳብ ከራሱ ጋር እንዲያዋህድ ሁሉን አውቃለሁ ከሚያሰኝ አባዜም አጽድቶ ትንሽ የማንበብና አዋቂዎች የሚሉትን የመስማት ትእግስትና ብልህነት ይስጠው።  አሜን!

 

The post ኃይሌ ገብረሥላሴ የተቃርኖ – የስኬትና የውድቀት – ምልክት ሲሆን (በሀገሬ ክብሬ) appeared first on Zehabesha Amharic.


በአዲስ አበባና ዙሪያዋ ኢንፍሉዌንዛ መከሰቱ ተረጋገጠ

$
0
0

በዚካ ቫይረስ የተጠቁ ሰዎች እንደነበሩ የሚያሳይ ፍንጭ አለ

downloadበአሁኑ ወቅት በአዲስ አበባና በአዲስ አበባ ዙሪያ ጉንፋን መሰል ኢንፍሉዌንዛ (A, B, H1N1) መከሰቱ በተደረጉ ሳምንታዊ ቅኝቶች መረጋገጡን፣ ጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ዓርብ ጥር 27 ቀን 2008 ዓ.ም. በሰጠው መግለጫ አስታወቀ፡፡

የኢትዮጵያ ኅብረተሰብ ጤና ኢንስቲትዩት ምክትል ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ዳዲ ጂማ እንደተናገሩት፣ በጥር ወር በአዲስ አበባ በሚገኙ የተለያዩ የጤና ተቋማት ላይ ኢንስቲትዩቱ ባደረጋቸው ሳምንታዊ ቅኝቶች 32 ሰዎች በኢንፍሉዌንዛ መያዛቸው፣ ከእነዚህ ውስጥ አራቱ ሕይወታቸው ማለፉ ታውቋል፡፡ አራቱን ሰዎች ግን ለሕልፈት ያበቃቸው ኢንፍሉዌንዛው ብቻውን ሳይሆን፣ እንደ ሳንባና ስኳር ያሉ ሕመሞች ስለነበሩባቸው እንደሆነ አስረድተዋል፡፡
የዚህ ዓይነቱ ኢንፍሉዌንዛ ከዚህ ቀደምም ወቅቱን እየጠበቀ ይከሰት እንደነበረው ዓይነት እንጂ፣ ምንም የተለየ ነገር አለመኖሩንም ዶ/ር ዳዲ ገልጸዋል፡፡ ይሁን እንጂ በኅብረተሰቡ ብቻም ሳይሆን በሕክምና ባለሙያዎች በኩል ጭምር ሥጋትና መደናገጥ ታይቶ እንደነበር ዶ/ር ዳዲ አክለዋል፡፡ ዶ/ር ዳዲ ኢንፍሉዌንዛው ከዚህ ቀደምም የታየና ወቅት እየጠበቀ የሚከሰት ከሆነ የሕክምና ባለሙያዎችን ጭምር እንዴት ሊያደናግጥ ይችላል? የሚል ጥያቄ ቀርቦላቸው ሲመልሱ፣ ‹‹በማኅበራዊ ድረ ገጾች ላይ የታዩና ኅብረተሰቡ ላይ ሥጋት የፈጠሩ መረጃዎች የሕክምና ባለሙያዎች ላይም ተፅዕኖ አሳድረዋል፤›› ብለዋል፡፡
የኢንፍሉዌንዛ መከሰትን ተከትሎ ለሕክምና ባለሙያዎች ሥልጠና መሰጠቱን የገለጹት ዶ/ር ዳዲ፣ አሁንም ቅኝቱ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አስታውቀዋል፡፡ በተጨማሪም ናሙናዎች ለተጨማሪ ምርመራ አሜሪካ ወደሚገኘው ሴንተር ፎር ዲዚዝ ኮንትሮል (CDC) መላካቸውን ጠቁመዋል፡፡

ዶ/ር ዳዲ እንደገለጹት፣ ናሙናዎች መላካቸው ለዚህ ኢንፍሉዌንዛ ተብሎ ሳይሆን የተለመደ አሠራር ስለሆነ ነው፡፡ ከኢንፍሉዌንዛው ጋር በተያያዘ አስፈላጊውን ምርመራ ማድረግ የሚያስችል ላቦራቶሪ ኢትዮጵያ ውስጥ መኖሩን አረጋግጠዋል፡፡ ኢንፍሉዌንዛውን ለማከምም የሕክምና ባለሙያዎች የሚከተሉት መደበኛውን፣ አስፈላጊውንና መሠረታዊ በሽታ የመከላከል ፕሮቶኮል እንደሆነ ዶ/ር ዳዲ ገልጸዋል፡፡
ምንም እንኳ ኢንፍሉዌንዛው የተከሰተው አዲስ አበባና በዙሪያዋ መሆኑ ቢገለጽም፣ በቅኝቱ በኢንፍሉዌንዛ መያዛቸው ከተረጋገጠው 32 ሰዎች መካከል የተወሰኑት በሪፈራል ከተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች ወደ አዲስ አበባ የመጡ መሆናቸው ታውቋል፡፡

በሌላ በኩል ከቀናት በፊት የዓለም ጤና ድርጅት ዓለም አቀፍ የጤና ሥጋት ነው ያለው የዚካ ቫይረስ፣ ከሁለት ዓመታት በፊት ለሌላ ምርመራ በተወሰዱ ናሙናዎች ላይ በተደረገ ምርመራ፣ በቫይረሱ የተጠቁ ሰዎች እንደነበሩ ፍንጭ መገኘቱን የጤና ጥበቃ ሚኒስትሩ አማካሪ ዶ/ር መርዓዊ አረጋዊ ለጋዜጠኞች ገልጸዋል፡፡ በሽታውን የሚያስተላልፉ ትንኞች በማንኛውም ሞቃት የአየር ንብረት ክልል በብዛት የሚገኙ በመሆናቸው፣ በአፍሪካ ቫይረሱ ሊገኝ እንደሚችል ጥርጣሬ መኖሩን መረጃዎች ይጠቁማሉ፡፡

ከሁለት ዓመት በፊት የተገኘው ፍንጭ በአሁኑ ወቅት ስላለው ሁኔታ የሚናገረው እንደሌለ የገለጹት ዶ/ር መርዓዊ፣ ኅብረተሰቡ በተለይም ነፍሰጡሮች ትንኝን መከላከል እንዳለባቸው አሳስበዋል፡፡
ዶ/ር መርዓዊ እንደገለጹት ዚካ ቫይረስ በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ ሥጋት ባይሆንም፣ የቫይረሱን መኖር አለመኖር መመርመር የሚያስችል ኬሚካል በጥቂት ቀናት ውስጥ ወደ አገር ውስጥ ይገባል ምርመራውን ማድረግም ይጀመራል፡፡

Source:: Ethiopian Reporter

The post በአዲስ አበባና ዙሪያዋ ኢንፍሉዌንዛ መከሰቱ ተረጋገጠ appeared first on Zehabesha Amharic.

ሻለቃ ኃይሌ አፍሪካን እንደሰቀላት አውርዶ ፈጠፈጣት?

$
0
0

ሰሞኑን ሻለቃ ኃይሌ ገ/ሥላሴ ለአንድ የውጪ ጋዜጠኛ “ዲሞክራሲ (መስፍነ ሕዝብ) ለአፍሪካ አያስፈልጋትም! ለአፍሪካ የሚያስፈልጋት መልካም አሥተዳደር ነው!” ብሎ መናገሩን ሰምተናል፡፡ እንደሰማንም በእጅጉ አፍረናል ተሸማቀናልም፡፡ እኔ በበኩሌ “እንዲያው ይሄ ሰውየ እያሰበና ነገሮችን በቅጡ ተረድቶ ተገንዝቦ ገብቶት መናገር የማይችል ከሆነ ምናለ ዝም ቢል ባይናገርስ!” ብያለሁ፡፡

Haile

ይሄንን ንግግሩን “አይ እሱ ለማለት የፈለገው…” ብለን ልንለው የምንችለው ምንም ሌላ ነገር የለውም፡፡ በማያሻማ ንግግር ጥርት አድርጎ ነው የተናገረው፡፡ ትንሽ ግራ የሚያጋባው ያለ ዲሞክራሲ (መስፍነ ሕዝብ) እንዴት ተብሎ መልካም አሥተዳደር ሊመጣ እንደሚችልና እንዴት ሊነጣጠሉ እንደሚችሉ ማሰቡ ነው፡፡ ኃይሌ ሆይ! መልካም አሥተዳደር ሲባል ለአንተ ምን ማለት ነው የሚመስልህ? ዲሞክራሲስ?

ኃይሌ በዚህ ንግግሩ ለአፍሪካዊያን ያለውን ንቀትና ጥላቻ ቁልጭ አድርጎ አሳይቷል፣ ሰድቦ ለሰዳቢ አዋርዶ ለአዋራጅ ሰጥቶናል፡፡ ምዕራባዊያን ለእኛ ለአፍሪካዊያን ስር የሰደደ ከባድ ጥላቻና ንቀት እንዳለባቸው ይታወቃል፡፡ ኃይሌ ውሎው ከእነሱ ጋር ሲሆን ጊዜ ፈረንጅ የሆነ መሰለው መሰለኝ እነሱ እኛን በሚያዩበት ዓይን ዓየንና የንቀትና የጥላቻ ጅራፉን አጮሆ ክፉኛ ሞሸለቀን፡፡ እውነትም ለካ እግር ጭንቅላት አይሆንም፡፡

እኔ የኃይሌ ስኬት እግሩና ጭንቅላቱ በመቀናጀት ያመጡት ያስገኙለት ይመስለኝ ነበር፡፡ ሰውየውን በተደጋጋሚ እንደታዘብነው ይህ ግምት የተሳሳተ እንደሆነ አሳይተውናል፡፡ ኃይሌ በዓለም አቀፍ መድረኮች ባስገኛቸው በርካታ አንጸባራቂ ድሎች አፍሪካን በእጅጉ አኩርቶ ነበር፡፡ ኃይሌ በዘረኛ ነጮች ዘንድ አፍሪካዊያን ከእኛ በእኩል ብሎም በተሻለ ሊሠሩት የሚችሉት ምንም ነገር የለም!፣ ተናጋሪ እቃ ናቸው ወዘተረፈ.” የሚለውን የተሳሳተና የደነቆረ አስተሳሰብ የተሳሳተ እንደሆነ ካረጋገጡ ብርቅየ የአፍሪካ ልጆች አንዱ ነበር፡፡ ልብ በሉ ነበር ነው ያልኩት ነው አላልኩም፡፡ ነው የሚባለው ያ ሰው የገነባውን እንደገነባ የቀረ እንደሆነ ነው፡፡ የገነባውን ካፈረሰው ግን ነው ሳይሆን የሚባለው ነበር ነው የሚባለው፡፡

ኃይሌ በዚህ ጸያፍና የደነቆረ አነጋገሩ ልክ እንደ ዘረኛ ነጮች ሁሉ አፍሪካዊያን ከሌሎቹ ሕዝቦች ጋር እኩል እንዳልሆንንና እኩል መሆንም እንደማይገባን ነግሮናል፡፡ በእውነቱ በእጅጉ እናዝናለን!

እኔ ኃይሌ “ይቻላል!” ብሎ ሲል አንድ እራሱን ብቻ ሳይሆን በብዙ ዓይነት ፈተናዎች ተኮድኩዶ የተያዘውን መላውን የጥቁር ሕዝብ እያሰበ የሚናገረው መሪ ቃል “slogan” ይመስለኝ ነበር፡፡ ለካ ሰውየው የሚመስለንን ያህል ብስል ሰው አልነበረም ላካ “ይቻላል!” ብሎ ሲል እራሱንና እራሱን ብቻ በማሰብ ኖሯል ይሄንን ወርቃማ ቃል ይናገር የነበረው፡፡

አሁን ኃይሌ ይቻላልን ወደ አይቻልም ቀይሮታል፡፡ ወደፊት ኃይሌ ምንም ዓይነት ኪሳራ ቢደርስበት ከዚህ በላይ ኪሳራ ይደርስበታል ብየ አንገምትም፡፡ ወዳጅነቱም ከአንባገነን የአፍሪካ መሪዎች ጋር ነው እንጅ ከመከረኛና ጭቁን የአፍሪክ ሕዝብ ጋር አይሆንም፡፡

ዛሬ ኃይሌ ፈረንጅ ነው ይህ የተናገረው ጸያፍ የድፍረትና የንቀት ቃልም እሱን አይመለከትም፡፡ ምናልባት ወደፊት እራሱን በትኩረት ለመመልከት የሚያስችል አቅልና ዕድል ካገኘ አካሉ ጥቁር አፍሪካዊ መሆኑን ያይና በተናገረው ነገር ያፍር ይሸማቀቅም ይሆናል፡፡

“ሲያልቅ አያምር” አሉ ትላንትና በኮራንበት ወገናችን ዛሬ አፍረንበታልና ኃዘን ተሰምቶኛል፡፡ አፍሪካዊያን ወንድሞቻችን ይሄንን የኃይሌን ንግግር ኃይሌ ኢትዮጵያዊ በመሆኑ “ኢትዮጵያዊያን ለእኛ ለአፍሪካዊያን ንቀት አላቸው” ብለው በሚያስቡት አውድ እንደተናገረው አስበው በእሱ ስሕተት መላው ኢትዮጵያዊ የሚጠላ መሆኑን ሳስብም እራሴን ያመኛል፡፡ ልቡናውን ይስጥልና ሌላ ምን ይባላል?

ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር!!!

ሠዓሊ አምሳሉ ገ/ኪዳን አርጋው

The post ሻለቃ ኃይሌ አፍሪካን እንደሰቀላት አውርዶ ፈጠፈጣት? appeared first on Zehabesha Amharic.

Sport: 26ኛው ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪምየር ሊግ: አርሰናል የመሪነት ትንቅንቁን ተቀላቀለ ፤ ማን ዩናይትድ ካለፉት 10 ጨዋታዎች ማሸነፍ የቻለው 3ን ብቻ ነው

$
0
0

dani

(ዘ-ሐበሻ) 26ኛው ሳምንት የ እንግሊዝ ፕሪምየር ሊግ ትናንት እና ዛሬ ቀጥሎ ውሏል:: በሳምንቱ የፕሪምየር ሊጉ ጨዋታዎች ያልተጠበቁ ውጤቶች ተከስተዋል:: ፕሪምየር ሊጉን በ53 ነጥቦች እየመራ የሚገኘው ሌስተር ሲቲ በባከነ ሰዓት በአርሰናል በተቆጠረበት ጎል ቢሸነፍም አሁንም ፕሪምየር ሊጉን እየመራ ይገኛል::

በዳኒ ዌልቤክ የባከነ ሰዓት ጎል ያሸነፈው አርሰናል በ2ኛነት ፕሪምየር ሊጉን እየተከተለ የመሪነት ትንቅንቁን ተቀላቅሏል:: ሌስተር ሲቲ በፕሪምየር ሊጉ አርሰናልን ከ1994 ወዲህ አሸንፎ አያውቅም:: የአርሰናሉ አሰልጣኝ አርሰን ዌንገር ስለዚህ ጨዋታ አስተያየታቸውን ሲሰጡ “ሌስተሮች በመከላከል በኩል ጥሩ ነበሩ:: እስከ እረፍትም 1ለ0 እየተመራ ነበር:: ሌስተሮች በመከላከሉ በኩል ጥሩ ባይሆኑ ኖሮ ብዙ ጎሎችን እናስቆጥር ነበር” ብለዋል::

united

በዘንድሮው ፕሪምየር ሊግ አሰልቺ ጨዋታ እያደረገ ነው እየተባለ በስፖርት ተንታኞች ዘንድ የሚተቸው ማን.ዩናይትድ አሁንም ሽንፈትን አስተናግዷል:: ትናንት በጥቋቁሮቹ ድመቶች 2ለ1 ተሸንፈዋል:: ሰንደርላንድ በፕሪምየር ሊጉ ወራጅ ቀጠና ላይ ያለ ቢሆንም ማን.ዩናይትድን አሸንፈውታል:: ማን.ዩናይትድ ባለፉት 10 የፕሪምየር ሊግ ጨዋታዎች ውስጥ ማሸነፍ የቻለው 3 ጊዜ ብቻ ሲሆን; 3 ጊዜ አቻ ወጥቶ 4 ጊዜ ተሸንፏል::

በሌሎች ጨዋታዎች ሊቨርፑል አስቶንቭላን ግማሽ ደርዘን ጎል አስቆጥሮበት 6ለ0 አሸንፎታል::
በርንዝማውዝ በስቶክ 3ለ1 ተሸንፏል:: ቸልሲ ኒውካስትልን 5ለ1.. ዌስትብሮም ኤቨርተንን 1ለ0; ዋትፎርድ ክርስታል ፓላስን 2ለ1 እንዲሁም ሳውዛምፕተን ስዋንሳን 1ለ0 ሲያሸንፉ ኖርዊች እና ዌስትሃም 2ለ2 ተለያይተዋል:: ይህ ዜና እየተጻፈ ባለበት ወቅት ማንቸስተር ሲቲ እና ቶተንሃም እየተጫወቱ ነው:: የሆለቱ አሸናፊ ፕሪምየር ሊጎን በ3ኝነት ይመራል::

The post Sport: 26ኛው ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪምየር ሊግ: አርሰናል የመሪነት ትንቅንቁን ተቀላቀለ ፤ ማን ዩናይትድ ካለፉት 10 ጨዋታዎች ማሸነፍ የቻለው 3ን ብቻ ነው appeared first on Zehabesha Amharic.

Health: ቦርጭን ለማጥፋት የሚረዱ 10 መንገዶች እነሆ

$
0
0

health

(በዳንኤል አማረ ©ኢትዮጤና)

1. ስኳርን ወይም ጣፋጭ ነገርን ይቀንሱ፡፡
2. ጤናማ የሆነ ስብ(ፋት) ይውሰዱ፡፡
3. ነጭ ካርቦሃይድሬት አይጠቀሙ፡፡
4. ከሁለት እስከ ሶስት ሊትር ውሃ በቀን ይጠጡ፡፡
5. ጭንቀትን ይቆጣጠሩ (ኮርቲሶልን መቀነስ)፡፡
6. አረንጓዴ ቅጠላ ቅጠል የሆኑ አትክልቶችን ይመገቡ፡፡
7. ቀላልና ጤናማ የሆነ ፕሮቲን ይመገቡ (ለምሳሌ ነጭ ሥጋ ያልሆነ)፡፡
8. ሰውነትዎን ያንቀሳቅሱ ወይም ስፖርታዊ እንቅስቃሴ ያድርጉ፡፡
9. ለብ ባለ ውሃ ውስጥ ሎሚ ጨምቀው ይጠቀሙ፡፡
10. ያለዎትን ሰውነት በመውደድ የሚመኙትን አይነት ሰውነት እንዲኖርዎ ይስሩ፡፡

መልካም ጤንነት!!

The post Health: ቦርጭን ለማጥፋት የሚረዱ 10 መንገዶች እነሆ appeared first on Zehabesha Amharic.

ዳና ድራማ ክፍል 16

Viewing all 15006 articles
Browse latest View live