Quantcast
Channel: Ethiopian News | ዘ-ሐበሻ | Latest News Provider | News For All
Viewing all 15006 articles
Browse latest View live

የትግል ስትራቴጂ ምንነት እና የትግል ስትራቴጂ መረጣ (ክፍል ሶስት: የመጨረሻ)

$
0
0

ታደሰ ብሩ

3. የትኛው የትግል ስትራቴጂ ይበጀናል? ለምን?

strategic-goals_satenawበኢትዮጵያ ፓለቲካ ውስጥ የፓለቲካ ፓርቲዎች ከታወቁበት 1960ዎቹ መጨረሻ ጀምሮ እስከዛሬ ድረስ የፓለቲካ ፓርቲዎችን ካወዛገቡ ትላልቅ ርዕሶች አንዱ የትግል ስትራቴጂና ስልት ምርጫ ነው። ለምሳሌ ትጥቅ ትግልን እንደ ስትራቴጂ በመውሰድ ላይ ተስማምተው እያለ “የከተማ ትጥቅ ትግል” ወይስ “የገጠር ትጥቅ ትግል” በሚል የስልት ልዩነት የተፋለሱ፣ ከዚያም አልፎ የተገዳደሉ ድርጅቶችና ስብስቦች መኖራቸው የቅርብ ጊዜ ታሪክ ነው ። ዛሬም ፓለቲካችን ውስብስብ ችግር ውስጥ ካስገቡት ጉዳዮች አንዱ ወያኔን በማስወገድ አስፈላጊነት ላይ የሚስማሙ ድርጅቶች በስትራቴጂና በስልቶች ላይ ስምምነት የሌላቸው መሆኑ ነው።

የስትራቴጂ ምርጫ በንድፈ ሀሳብም በተግባርም ውስብስብ ሂደት ይጠይቃል። ከሁሉ አስቀድሞ በአማራጮቹ ዝርዝር ላይ መስማማት ያስፈልጋል። ቀጥሎ ደግሞ መመዘኛዎችን ማውጣትና በመመዘኛዎች ላይ መስማማት ያስፈልጋል። ከዚያ ቀጥሎ ደግሞ በመመዘኛዎቹ አለካክ (methodology) ላይ መስማማት ይጠይቃል። በመጨረሻም በውሳኔ ህግ (decision rule) ላይ መስማማት ይጠይቃል።

ነገሩን ለማሳጠር በአማራጭ ስትራቴጂዎች ዝርዝር ተስማማን እንበልና ከቀረቡት አማራጭ ስትራቴጂዎች የተሻለውን በምን መመዘኛ ነው የምንመርጠው ብለን እንጠይቅ። ለስትራቴጂ መረጣ ብዙ መመዘኛዎችን መዘርዘር ብንችልም በሶስት ዋና ዋና መመዘኛዎች ማጠቃለል ይቻላል። እነዚህም 1ኛ) ተስማሚነት (Suitability)፣ 2ኛ) ተፈፃሚነት (Feasibility)፣ እና 3ኛ) ተቀባይነት (Acceptability) ናቸው።

ተስማሚነትን በተመለከተ ቁልፍ ጥያቄ መሆን ያለበት “በአማራጭነት የቀረበው ስትራቴጂ እተፈለገው ግብ ያደርሳል ወይስ አያደርስም?” የሚለው ጥያቄ ነው። የዚህ ጥያቄ መልስ አሉታዊ ከሆነ አማራጭ ተብሎ የቀረበው ስትራቴጂ እውነተኛ አማራጭ አይደለም ማለት ስለሚሆን በዝርዝሩ መውጣት አለበት። ትንሽም እንኳን እድል ካለው በምርጫው ውስጥ ቆይቶ የሚከተሉት ጥያቄዎች መመለስ ይሆርበታል። ይህ ስትራቴጂ እኛ አገር ውስጥ ይሠራል ወይ? ግልጽ ነው ወይ? ለባህላችን፣ ለአኗኗራችን ተስማሚ ነው ወይ?

ተፈፃሚነትን በተመለከተ መጠየቅ ያለባቸው ጥያቄዎች የሚከተሉትን የመሰሉ ናቸው። ለስትራቴጂው የሚያስፈልገውን ግብዓት ማግኘት ይቻላል ወይ? ለምሳሌ ስትራቴጂው የሰለጠኑ ሰዎችን የሚፈልግ ከሆነ እነሱን ማግኘት ይቻላል ወይ? በርካታ ሰው በአንዴ “ሆ” ብሎ መነሳት የሚኖርበት ከሆነ ይህንን ማምጣት ይቻላል ወይ? ስትራቴጂው የሚፈልገው ድርጅታዊ ብቃት አለ ወይ? ስትራቴጂው የሚፈልገው አመራር አለ ወይ? የተፈፃሚነትን መመዘኛ በሁለት አንኳር ነጥቦች ማጠቃለል ይቻላል – ሀ) አዋጪነት – ምን ያህል ዋጋ ያስከፍላል? ለ) አስተማማኝነት – ስትራቴጂው የሚፈልገውን ግብዓት (ሰው፣ አመራርና ድርጅት) መፍጠር ይቻላል?

ተቀባይነትን በተመለከተ ደግሞ ስትራቴጂው በዋና ዋና ባለድርሻ አካላት “ፍትሀዊ ነው” ተብሎ ይታሰባል ወይ? ማኅበረሰቡ “መልካም” የሚለው ዓላማ “መልካም ባልሆነ” ስትራቴጂ ተግባራዊ ቢደረግ በዓላማውን መልካምነት ላይ ተጽዕኖ አለው? ለምሳሌ፣ አምባገነን አገዛዝን ኃላፊነት በሚሰማው አመራር መቀየር መልካም ነገር ነው። ይህ ሽግግር በሰላማዊ መንገድ ቢፈፀም እጅግ በጣም ጥሩ ነው። ሆኖም ግን ይህ ሳይቻል ቀርቶ አምባገነኑ አገዛዝ በጉልበት ተቀይሮ ኃላፊነት የሚሠማው አመራር ሥልጣን ላይ ቢወጣ ሽግግሩ የተደረገበት መንገድ በአዲሱ አመራር ተቀባይነት ላይ ያለው ተጽዕኖ ምንድነው? “መልካም” የሆነው ዓላማ ከሞራል አንፃር ተመራጭ ባልሆነ ስትራቴጂ አማካይነት ተፈፃሚ ሆኖ መልካምነቱን እንደያዘ ማቆየት ይቻላል ወይ?

ከላይ የተዘረዘሩት የስትራቴጂ አማራጮች በሙሉ የመጀመሪያውን የማጥሪያ ጥያቄ ማለፍ አለባቸው። የማጥሪያው ጥያቄ “ይህ ስትራቴጂ ወያኔን ማስወገድ ይችላልን” የሚል መሆን ይኖርበታል። ይሄንን ቁልፍ ጥያቄ በአዎንታ ያልመለሰ ስትራቴጂ ይሰረዛል። (ለመሰረዝ መቸኮል እንደሌለብን አስቀድመን ተናግረናል)። ይህንን መመዘኛ ያለፉ ስትራቴጂዎች ሁሉ በእነዚህ ሶስት መመዘኛዎች ሊለኩ ይችላሉ። ለምሳሌ ከላይ በምሳሌነት ያቀረብናቸውን አምስት ስትራቴጂዎች በሰንጠረዥ 1 በተመለከተው መሠረት ለምዘና ልናዘጋጃቸው እንችላለን።

ሰንጠረዥ 1 በዚህ ሁኔታ ከተጋጀ በኋላ በእያንዳንዱ መመዘኛ አንፃር ከ 1 -10 ወይም 1 -100 ውጤት ሰጥተን ደምረን የተሻለውን እንመርጣለን።

ሰንጠረዥ 1ን ለመሙላት ሰፊ ውይይት የሚጠይቅ መሆኑ ምንም ጥርጥር የለውም። የዚህ ዘዴ አንዱ ጥቅምም ሥርዓት ላለው ውይይት የሚያዘጋጅ መሆኑ ነው። ለምሳሌ ለባህላችን፣ ለአኗኗራችን ለታሪካችን ተስማሚ የሆነው ሰላማዊ ትግል ነው? ወይስ የትጥቅ ትግል? የሚለው ጥያቄ ብዙ የሚያወያይ ነው።

ወደ ስትራቴጂዎቹ እንመለስና ስትራቴጂ 1 ላይ እናትኩር። ሰላማዊና ህጋዊ ትግል እንደ ስትራቴጂ ተስፋ አለው ማለት ህወሓት የሚቆጣጠረው ፓርላማ ባወጣቸው ህጎች እየተገዙ፤ ህወሓት የሚቆጣጠረው ፍርድ ቤት የሚሰጠውን ውሳኔ እያከበሩ፤ በህወሓት ፓሊስና ጦር ሠራዊት ቁጥጥር ስር ተኩኖም ቢሆን ህወሓት የሚቆጣጠረው የምርጫ ቦርድ በሚያስተዳድረው ምርጫ ራሱ ህወሓትን ማሸነፍ ይቻላል ብሎ ማመን ነው። እኔ በበኩሌ ይኼ ተስፋ የሌለው ስትራቴጂ ነው ብዬ ስለማምን እሰርዘዋለሁ። የዚህኛው ስትራቴጂ መሰረዝ ደግሞ አራተኛውን ስትራቴጂ ማለትም “የትጥቅ ትግል እና ሰላማዊና ህጋዊ ትግል ማቀላቀል” የሚለው ላይም የጥያቄ ምልክት ያስቀምጥበታል፤ ወይም ከአቢይ ስትራቴጂነት “በዚህ ስትራቴጂ ከሚያምኑ ድርጅቶች ጋር እንደምን ያለ የወዳጅነት ግኑኝነት ይኑረኝ? ወደሚል የሕዝብ ግኑኝነት ስትራቴጂነት ያወርደዋል።

የኔ እምነት ለሚጋራኝ የቀሩት ስትራቴጂዎች ሶስት ብቻ ናቸው (ሰንጠረዥ 2 ይመልከቱ)። ለኔ ያሉኝ አማራጮች 2፣ 3 እና 5 ናቸው። እነሱም ስትራቴጂ 2: ሰላማዊ ሆኖም ግን ህገወጥ ትግል፤ ሰትራቴጂ 3: ትጥቅ ትግል፣ እና ሰተራቴጂ 5: ትጥቅ ትግል እና ሰላማዊ ሆኖም ግን ህገወጥ ትግል ተቀላቅሎ ። እያንዳንዱን ለየብቻ እያነሳን እንነጋገርባቸው።

3.1. ሰላማዊ ሆኖም ግን ህገወጥ ትግል እንደ ስትራቴጂ

ሰላማዊ ሆኖም ግን ህገወጥ ትግል እንደ ስትራቴጂ መውሰድ ማለት የአገዛዙን ህጎችንና ደንቦችን እየጣሱ “እምቢ አልገዛም” ብሎ በማመጽ ህወሓትን ከስልጣን ማስወገድ ይቻላል በሚል እሳቤ ላይ የተመረኮረዘ ነው። ይህ ስትራቴጂ ይበልጥ የሚታወቀው ሕዝባዊ እምቢተኝነት (Civic Disobedience) በሚል መጠሪያ ነው። ከዚህ በኋላ እኔም “ሕዝባዊ እምቢተኝነት” የሚለውን መጠሪያ እጠቀማለሁ።

በርካታ አምባገነን መንግሥታት በሕዝባዊ እምቢተኝነት መንኮታኮታቸው እውነት ነው። የቅርቦቹን ብቻ በምሳሌነት ብናነሳ እንደ አውሮፓውያን አቆጣጠር በ1980ዎቹ መጨረሻ የቀድሞ ሶቭየት ኅብረት ግዛቶች የነበሩ በኢስቶኒያ፣ ላትቪያና ሊቷንያ፤ በምሥራቅ አውሮፓ በፓላንድ፣ በቼክ ሪፑብሊክ፣ በስላቫኪያና በምሥራቅ ጀርመን፤ በእስያ በፊሊፒንስ እና በላቲን አሜሪካ ቮሊቪያ ውስጥ አምባገነን ሥርዓቶች ተንኮታኩተዋል። ከዚያም እአአ በ2003 ጽጌረዳማ አብዮት የሚል ስያሜ በአገኘው የጆርጂያ አብዮት፤ በ2005 “ብርቱካናማ አብዮት” የሚል ስያሜ የተሰጠው የዩክሬይን አብዮት፤ በ2005 “ሲዳር አብዮት” በተባለው የሊባኖስ አብዮት አገዛዞች ተቀይረዋል። ከዚያም በ2011 በቱኒዝያና በግብጽ “ጃዝሚን አብዮት” የተባለው ተካሂዶ የቤን ዓሊንና የሆስኒ ሙባረክ አገዛዞች ተወግደዋል። በመጨረሻም አምና በ2014 በቡርኪና ፋሶ በሁለት ቀናት አብዮት ከሃያ ዓመታት በላይ የተንሰራፋው አገዛዝ ተንኮታኩቷል። ከዚህ አጭር ዳሰሳ መረዳት እንደምንችለው ሕዝባዊ እምቢተኝነት ውጤታማ የሆነባቸው የቅርብ ጊዜዓት ምሳሌዎችም በሁሉም ክፍለዓለማት የሚገኙ መሆኑን ነው።

በአንፃሩ ደግሞ ሕዝባዊ እምቢተኝነት ተሞክሮባቸው የከሸፉ ወይም በሕዝባዊ እምቢተኝነት ተጀምረው ወደ ትጥቅ ትግል የዞሩ ምሳሌዎችም አሉ። በሕዝባዊ እምቢተኝነት የቅርብ ጊዜ ምሳሌነት ሲወደስ የነበረው የዩክሬኑ ብርቱካናማ አብዮትም በየጊዜው እያመረቀዘ አገሪቷን ወደ መከፋፈል አድርሷት እስካሁንም መቋጫ አላገኘም። በ2011 በሊቢያ የተቀሰቀሰ ሕዝባዊ እምቢተኝነት ወደ እርስ በርስ ጦርነት ተሸጋግሮ ኃያላን አገሮች ወደተሳተፉበት አውዳሚ ጦርነት ተሸጋግሯል። በሶሪያ የተቀሰቀሰው ሕዝባዊ እምቢተኝነት ዓለምን አደጋ ላይ ወደ ጣለ የእርስ በርስ ጦርነት ዘቅጧል። በየመን የተቀሰቀሰው ሕዝባዊ እምቢተኝነት ወደ እርስ በርስ ጦርነት ተሸጋግሮ አገሪቷን እያወደመ ከመሆኑም በላይ የአካባቢው አገሮች ሳይቀር ወደ ጦርነት እየሳበ ይገኛል።

ከላይ ለስትራቴጂዎች መመዘኛነት ያስቀመጥናቸው ሶስት መለኪያዎች- ተስማሚነት (Suitability)፣ ተፈፃሚነት (Feasibility) እና ተቀባይነት (Acceptability) አንፃር ሕዝባዊ እምቢተኝነት በምን ሁኔታዎች እንደሚሠራ በምን ሁኔታዎች ደግሞ እንደማይሠራ በማጥናት ከሀገራችን ተጨባጭ እውነታ ጋር ማገናዘብ ይጠበቅብናል። ይህ ሰፊ ምርምር የሚጠይቅ ሥራ በመሆኑ በዚህ ጽሁፍ የማይሞከር ነው። ሆኖም ዝርዝር ትንተና ውስጥ ሳንገባ ጠቅለል ያሉ ሀሳቦችን መስጠት ይቻላል።

የኢትዮጵያ ሕዝብ ተከታታይ በሆኑ አምባገነን ሥርዓቶች ሲበደል ቆይቷል። ቢያንስ በሶስት ተከታታይ ሥርዓቶች በመልካም አስተዳደር እና በልማት ስም ሲሸነገል ቆይቷል። ጥቂት ትላልቅ፤ በርካታ ትናንሽ አብዮቶች የከሸፉበት ሕዝብ ነው። የህወሓት አገዛዝ በሰላማዊ ሕዝባዊ እምቢተኝነት ቢቀየር ለውጡ የሚኖረው ተቀባይነት እና ከለውጡ በኋላ የሚመጣው መንግሥት የሚኖረው የሕዝብ ድጋፍ ከፍተኛ እንደሚሆን መገመት ቀላል ነው። ምንም እንኳን ማስተማመኛ ባይኖርም በእንዲህ ዓይነት መንገድ የመጣ መንግሥት ወደ ዲሞክራሲያዊ አስተዳደር የሚያደርገው ሽግግር በአንፃራዊ መልኩ ቀና ይሆንለታል ብሎ ተስፋ ማድረግ ይቻላል። በዚህም ምክንያት ሕዝባዊ እምቢተኝነት የሚኖረው ተስማሚነት ከፍተኛ ነው ብሎ ማመን ይቻላል።

ተፈፃሚነትን በተመለከተ ግን ሁኔታው ከዚህ የተለየ ነው። እስካሁን ከታዘብነው ሕዝባዊ እምቢተኝነት ውጤታማ በሆነባቸው አገሮች ውስጥ የሚከተሉት ሶስት ነገሮች ተሟልተዋል። (1) በራስ መተማመንን ያጎለበተ ሕዝብ፣ (2) አንፃራዊ ነፃነት ያላቸው ተቋማት እና (3) በብልሃት የተቀመሩ የትግል ስልቶች። እነዚህ ሶስት ነገሮች በአገራችን ተሟልተዋልን (ወይም በአጭር ጊዜ ሊሟየሉ ይችላሉን) ብለን ስንጠይቅ የምናገኘው ምላሽ የሚያረካ አይሆንም።

በራስ መተማመንን በተመለከተ ሁኔታዎች በፍጥነት እየተቀየሩ ነው። የማኅበረሰቡን ጥቅምና ስሜት በከፍተኛ ሁኔታ የሚነኩ አጀንዳዎች ሲኖሩ ብዛት ያለው ሕዝብ አገዛዙን ለመጋፈጥ እንደሚደፍር በሙስሊም ወገኖቻችን የተራዘመ እንቅስቃሴና ከቅርብ ግዜ ወዲህ ደግሞ በኦሮሚያ ላይ አይተነዋል። መላውን የኢትዮጵያ ሕዝብ በተመሳሳይ ስሜት የሚያንቀሳቅስ ኮርኳሪ አጀንዳ ለማግኘት መጣር ይኖርበታል። ለዚህ ብዙ መሠራት አለበት።

አንፃራዊ ነፃነት ያላቸው ተቋማት ጉዳይ። በሕዝባዊ እምቢተኝነት አምባገነን አገዛዞች በተገረሰሱባቸው አገሮች ሁሉ የተወሰኑ ተቋማት አንፃራዊ ነፃነት ነበራቸው። ለምሳሌ በፓላንድና በቼክ ሪፑብሊክ የለውጡ ዋነኛ አራማጆች የሙያ ማኅበራት ነበሩ። እነዚህ የሙያ ማኅበራት አንፃራዊ ነፃነት ነበራቸው። በፓላንድ ከሠራተኛ ማኅበር በተጨማሪ የካቶሊክ ቤተክርስቲያን ለነፃነት ትግል ከፍተኛ አስተዋጽዖ አበርክታለች። በዩክሬንና በጆርጂያ ፓርላማዎች አንፃራዊ ነፃነት የነበራቸው በመሆኑ የሕዝቡን ትግል የሚደግፉ የፓርላማ አባላት ነበሩ። ዩክሬን ውስጥ የሕዝቡን ትግል በመደገፍ የተወሰኑ የፓርላማ አባላት ፓርላማው ውስጥ የረሀብ አድማ አድርገዋል። ጥቂት ቆይቶም አብላጫው የፓርላማ አባላት የትግሉ ደጋፊዎች ሆኑ። በቱኒዝያ፣ ግብፅና ቡርኪና ፋሶ ሕዝባዊ እምቢተኝነት ሊሳካ የቻለው በኃላፊነት ስሜት የሚንቀሳቀስ አንፃራዊ ነፃነት ያለው የጦር ሠራዊት ስለነበራቸው ነው። በሶስቱም አገራት ጦር ሠራዊቱ የሕዝቡን ጥያቄ ደግፎ ተንቀሳቅሷል። በብዙዎቹ አገራት የፍትህ፣ የሚዲያ እና የአካዳሚያ ተቋማት አንፃራዊ ነፃነት ነበራቸው።

ኢትዮጵያ ውስጥ ያለው ተጨባጭ ሁኔታ ግን ከዚህ በጣም የተለየ ነው። አገራችን ኢትዮጵያ ትንሽ እንኳን የነፃነት ሽውታ ያለበት አንድም ተቋም የላትም። የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት፣ የፍትህ አካላቱ፣ ሚዲያው፣ አካዳሚያው በአገዛዙ ከመታፈናቸው በተጨማሪ ዘረኛ በሆነ መንገድ በመደራጀታቸው አገራዊ እይታ እንዳይኖራቸው ተደርጓል። ሲቪል ማኅበራት ፈጽሞ እንዳይኖሩ ተደርጓል፤ ። የሃይማኖት ተቋማት የሥርዓቱ ተቀጥላ ተደርገዋል። ወያኔ በሲቪል ማኅበራት ላይ የዘመተው እንደማኅበረሰብ የመዝለቃችን ዋስትና የሆነው ማኅበራዊ ካፒታላችንን ለማጥፋት ነው። እናም ጉዳቱ የማኅበራቱ ተግባር መሰናከሉ ብቻ ሳይሆን በአባላቱ መካከል ሊዳብር ይችል የነበረዉ የመተማመን መጠን መጥፋቱም ጭምር ነው፡፡ ማኅበራዊ ካፒታልን ማውደም ግዑዝ ካፒታል (ለምሳሌ ድልድይን) ከማፍረስ እጅግ የባሰ ጉዳት ያስከትላል፡፡

ሕዝባዊ እምቢተኝነትን ውጤታማ ያደርጋሉ የሚባሉት ሶስቱም መሠረታዊ ግብዓቶች (በራስ መተማመንን ያጎለበተ ሕዝብ፣ አንፃራዊ ነፃነት ያላቸው ተቋማት እና በብልሃት የተቀመሩ የትግል ስልቶች) በተሟላ ሁኔታ አለመገኘታቸው ሕዝባዊ እምቢተኝነት ብቻውን እንደ ስትራቴጂ ቢወሰድ እምንፈልገው ድል ያደርሰናል ብሎ ለማመን እንዳይቻል ያደርጋል። ስትራቴጂው ተስማሚ ቢሆንም ግብዓቶች ይጎድሉታል።

ለማጠቃለል፤ ሕዝባዊ እምቢተኝነት እንደ ስልት ተስማሚነቱ (Suitability)እና ተቀባይነቱ (Acceptability) ከፍተኛ ነው፤ ተፈፃሚነቱ (Feasibility) ላይ ግን ጥርጣሬዎች አሉ። ይህ ስትራቴጅ ብቻውን ህወሓትን ጥሎ በምትኩ ፍትህ፣ ነፃነት፣ ዲሞክራሲና እኩልነት የሰፈነባት እና ሀገራዊ አንድነቷ የተረጋገጠ ኢትዮጵያን ለመገንባት ያስችላል ብሎ ማመን ይከብዳል።


3.2. ትጥቅ ትግል እንደ ስትራቴጂ

በአገራችን ታሪክ ውስጥ ጠመንጃና ስልጣን ከፍተኛ ቁርኝት አላቸው። አብዛኛዎቹ የስልጣን ሽግግሮች የተደረጉት በጠመንጃ ታግዘው ነው። ጦረኝነት ኢትዮጵያዊ ባህል ነው፤ የኢትዮጵያ ሕዝብ ጠመጃንና ባለጠመንጃን ያወድሳል። ስለዚህም ትጥቅ ትግል እንደ ስትራቴጂ ምናልባት በልሂቃኑ ዘንድ ካልሆነ በስተቀር በአብዛኛው የኢትዮጵያ ሕዝብ ዓይን የተቀባይነት ችግር የለበትም።

ተፈፃሚነትን በሚመለከት ደግሞ ወያኔ በትጥቅ ትግል የማይሸነፍበት ምክንያት የለም። ወያኔ የኃላያን አገሮች ድጋፍ ያለው መሆኑ፤ ጦሩን በዘረኛ መንገድ ማዋቀሩ እና በአለም ፓለቲካ የሽብርተኝነት ስጋት መኖሩ በትጥቅ የሚታገዙ የነፃነት ትግሎች የሚጠብቃቸው ተግዳሮት ቀድሞ ከሚታወቀው በላይ እንዲሆን አድርገዋል። ይህ ትግሉን ያከብደዋል እንጂ ወያኔ በጉልበት የማይሸነፍ ኃይል እንዲሆን አያደርገውም።

ተስማሚነትን በሚመለከት ግን ሁኔታው ለየት ይላል። “በጠመንጃ ወደ ስልጣን የመጣ ኃይል አገሪቱን ወደ ዲሞክራሲ ሊመራ ይቻላል ወይ?|” የሚለው ጥያቄ በቀላሉ የሚመለስ አይደለም። በዓለም ታሪክ ውስጥ በጠመንጃ ወደ ስልጣን መጥተው ወደ ሲቪል አስተዳደር (በአንዳንድ ሁኔታዎችም ወደ ዲሞክራሲያዊ አስተዳደር) የተሸጋገሩ ሥርዓቶች አሉ። ኮሎምቢያ በ1957፣ ቬንዙዌላ 1958፣ ቦሊቪያ 1997፤ ስፔን 1931፣ ቱርክ 1960፣ ፓርቹጋል 1974፣ ጋና 1979፣ በቅርቡ በ2014 ግብጽን (ከመሀመድ ሙርሲ በኃላ የአብዱል ፈታ ኤል ሲሲ በመንፈንቅለ መንግሥት መምጣት) እና ሌሎች በርካታ ምሳሌዎችን በመዘርዘር መከራከር ይቻላል። ታሪክ፣ ዜጎችን ፈጅተው የመጡ አምባገነኖች ወደ ሲቪል አስተዳደር ሲቀየሩ አይታለች፤ በአንፃሩ ደግሞ በሰላማዊ መንገድ በሕዝብ ይሁንታ ወደ ስልጣን መንበር ወጥተው አስከፊ አምባገነን የወጣቸውን ታውቃለች። በክፋቱ የሚታወቀው የሂትለር ናዚ መንግሥት ወደ ስልጣን የመጣው በምርጫ ነው፤ ስታሊንም ሌኒንን ተክቶ እንጂ ገልብጦ የመጣ አይደለም። በሰላማዊ መንገድ የመጣ መንግሥት ዲሞክራሲያዊ መሆኑን ማረጋገጥ እንደማይቻል ሁሉ በጠመንጃ የመጣ ሁሉ አምባገነን ይሆናል ብሎ ማጠቃለል አይቻልም። ወሳኙ ነገር ለውጡ በመጣበት ወቅት ያለው የኃይል ሚዛንና የጠንካራ ተቋማት መኖር ወይም አለመኖር ነው።

ኢትዮጵያ ውስጥ የዲሞክራሲ ተቋማት ይቅሩና አገራዊ ተቋማት እንኳን የሉም። አገራችንን እንደ አገር ሰብስበው የያዟት ተቋማት እየተዳከሙ ናቸው። ከአገራዊ ስሜት ጋር የሚፎካከር አካባቢያዊ ስሜት ፋፍቷል። ህወሓት በስልጣኑ ለመቆየት ሲል አጎራባች ማኅበረሰቦችን፤ የተለያዩ ሃይማኖት አማኞችን በአክራሪነት ስም ሲያጋጭ የቆየ በመሆኑ የትጥቅ ትግል ከቁጥጥር ካፈተለከ የት ሊያደርስ እንደሚችል መገመት ያስፈራል።

በዚህም ምክንያት የትጥቅ ትግል እንደ ስትራቴጂ ተፈፃሚ እና ተቀባይነት ያለው ቢሆንም ተስማሚነቱ አጠራጣሪ ነው።

3.3. ትጥቅ ትግል እና ሰላማዊ ሆኖም ግን ህገወጥ ትግል ተቀላቅሎ እንደ ስትራቴጂ

ከላይ ስለሕዝባዊ እምቢተኝነትና ትጥቅ ትግል የተገለፀውን በሰንጠረዥ 3 ተጠቃሎ ቀርቧል። በሰንጠረዥ 3 በግልጽ እንደሚታየው ሕዝባዊ እምቢተኝነትም ሆነ የትጥቅ ትግል ለየብቻቸው በስትራቴጂነት ሲቀርቡ የሚጎላቸው ነገር አለ።

ግባችን ወያኔን ማስወገድ ብቻ አይደለም፤ ከወያኔ በኋላ የምትኖረን ኢትዮጵያ ፍትህ፣ ነፃነት፣ እኩልነትና ዲሞክራሲ የሰፈነባት እና አገራዊ አንድነቷ የተረጋገጠ እንዲሆን እንፈልጋለን፤ የምንመርጠ የትግል ስትራቴጂ ወደዚህ የሚያደርሰን መሆን ይኖርበታል። አሁን ባለው ሁኔታ ሕዝባዊ እምቢተኝነትም ሆነ የትጥቅ ትግል ለየብቻቸው ወደዚህ ግብ ሊያደርሱን ይችላሉ የሚል እምነት የለኝም።

ሀገራዊ ተቋማት የሌሉ በመሆናቸው የመብት ጥያቄዎች ሀይማኖታዊ ወይም ክልላዊ ብቻ ሆነው እንዳይቀሩ፤ የመብት ጥያቄዎች በቂ ምላሽ የሚያገኙት የፓለቲካ ሥርዓቱ ሲለወጥ እና ዲሞክራሲያዊ አመራር ሲሰፍን እንደሆነ ሰፊ ግንዛቤ ሊያገኝ ይገባል። ከዚህም በተጨማሪ የኢትዮጵያ የጦር ሠራዊት በኢትዮጵያዊያን የተገነባ ነገር ግን በህወሓት የሚመራ ነው። ሠራዊቱ አመራሩን አስወግዶ ከኢትዮጵያ ሕዝብ ጎን እንዲቆም የሚረዳው አካል ያስፈልጋል። እነዚህን ወሳኝ ተግባራት ለመከወን ነው የታጠቀ ሕዝባዊ ኃይል የመኖሩ አስፈላጊነት ጎልቶ የሚወጣው።

“ትጥቅ ትግል እና ሰላማዊ ሆኖም ግን ህገወጥ ትግል ተቀላቅሎ እንደ ስትራቴጂ” ተብሎ የተገለፀው በአጭሩ “ሁለገብ የትግል ስትራቴጂ” የሚባለው ነው። ”ሁለገብ የትግል ስትራቴጂ” ሕዝባዊ እምቢተኝነትና የትጥቅ ትግል (ሕዝባዊ አመጽ) ተደጋግፈው እንዲሄዱ የሚያደርግ ስትራቴጂ ነው።

ነፃና አገራዊ ተቋማት ባለመኖራቸው ምክንያት የተፈጠረውን ክፍተት በመሙላት ረገድ እና ወያኔ በሕዝብ ላይ ያሰፈነውን ፍርሀት ለመግፈፍ የታጠቀ ሕዝባዊ ኃይል ከፍተኛ ወሳኝ ሚና ይኖረዋል። የሕዝባዊ እምቢተኝነት መኖር ሕዝብ የትግሉ ባለቤት እንዲሆን ያደርገዋል። “ሁለገብ ትግልን” ስትራቴጂ አድርገን ከወሰድን “ሕዝባዊ እምቢተኝነት” እና “ሕዝባዊ አመጽ” ወደ ስልትነት ይወርዳሉ። ይህ ማለት ወደተፈለገው ግብ የሚደረሰው ስትራቴጂው በሙሉ በተግባር ላይ ሲውል ነው እንጂ አንዱ ብቻውን ተግባራዊ ሲሆን አይደለም ማለት ነው። ሁለገብ ትግልን እንደስትራቴጄ ከመረጥን ሕዝባዊ እምቢተኝነትንም ሕዝባዊ አመጽንም ማደራጀትና መምራት ይኖርብናል፤ ከዚህም በላይ ሁለቱን ማቀናጀት ይገባናል።

በሁለገብ የትግል ስትራቴጂ ላይ የሚቀርቡ ሁለት ዓይነተኛ ትችቶች አሉ።

አንዱ የአመጽ ትግልን እና ሰላማዊ ትግልን ማደባለቅ አይቻልም፤ “ውሀና ዘይት” ናቸው የሚል ነው። እርግጥ ሁለቱ የትግል ስልቶች በሚፈልጉት የሰው ዓይነትም ሆነ አደረጃጀት የተለያዩ ናቸው። ይህ ማለት ግን እያንዳንዳቸው በየሚፈልጉት አደረጃጀት ተደራጅተው ሊደጋገፉ አይችሉም ማለት አይደለም። በመሠረቱ እስካሁን የሚታወቁ የነፃነት ትግሎች እና አብዮቶች ሁሉ ምጣኔዓቸው ይለያይ እንጂ የሕዝባዊ እምቢተኝነትና የሕዝባዊ አመጽ ድብልቆች ናቸው። ደቡብ አፍሪቃን ከአፓርታይድ ነፃ ያወጣው ትግል ሁለቱ ስልቶች ተደጋግፈውበታል። በምሥራቅ አውሮፓና በሰሜን አፍሪቃ የተካሄዱ የለውጥ እንቅስቃሴዎችም ቢሆኑ አመጽና እምቢተኝነት የተደባለቀባቸው አሊያም የተፈራረቁባቸው ነበሩ። እንዲያዉም ዛሬ ያለውን የሰሜን አፍሪቃና መካከለኛ ምሥራቅ ሁኔታ ስናጤን ለማስተዋል ከምንገደዳቸው መራር ሀቆች አንዱ በሕዝባዊ እምቢተኝነት አምባገነን አገዛዞች ተገርስሰው በምትካቸው ደካማ መንግሥታት ወደስልጣን ከመጡ የተራዘመ ቀውስ ሊከተል የሚችል መሆኑ ነው። ይህ እውነታ ከመጀመሪያው የተደራጀ ሕዝባዊ ኃይል መኖር አስፈላጊነትን ያጎላዋል።

ሁለተኛው ትችት ደግሞ “የትጥቅ ትግል መኖር አምባገነኞች ወታደራዊ ኃይላቸውን እንዲጠቀሙ መንገድ ይከፍትላቸዋል በውጤቱም የበርካታ ሕዝብ ሕይወት አደጋ ላይ ይወድቃል” የሚል ነው። ሁለገብ ትግል እንደትግል ስትራቴጂ በአማራጭነት የሚወሰድባቸው አገሮች ውስጥ ያሉ መንግሥታት ሠራዊታቸውን በሰላማዊ ሕዝብ ላይ ከማዝመት የማይመለሱ እንደ ህወሓት ዓይነት ያሉ አገዛዞች ናቸው። እነዚህ አገዛዞች የበዛ ጥፋት የሚያደርሱት ራሱን መከላከል የማይችል ሆኖም ግን ጠንክሮ የሚታገል ተቃዋሚ ሲገጥማቸው ነው። እንደዚህ ዓይነት አገዛዞች በሰላማዊ ሰልፈኞች ላይ ከመተኮስ የማይመለሱ በመሆናቸው በመለሳለስ ኪሳራ ማስቀነስ አይቻልምበመሠረቱ እኛም አገር ቢሆን ሰላማዊ ትግልና የአመጽ ትግል የሚያስከፍሉት ዋጋ መሳ ለመሳ ሆኗል ።

“ሁለገብ ትግል” ራሱ የብዙ ስትራቴጂዎች ጥቅል ስያሜ መሆኑ ማስታወስ ይበጃል። ለምሳሌ አንዳንድ ሰዎች “ክብሪቱን አንዴ ለኩሱልን እንጂ ከዛ ቀጥሎ ያለውን ለኛ ተውልን ይላሉ” ይህ አነገጋር ወደ ስትራቴጂ ሲመነዘር የሚከተውን ይመስላል: ህወሓት ከስልጣን የሚወገደው ሕዝባዊ አመጽና ሕዝባዊ እምቢተኝነት በፈረቃ በተግባር ላይ በሚወሉበት ሁለገብ ትግል ነው። የፈረቃው ቅደም ተከተልም በመጀመሪያ ሕዝባዊ ኃይል ወታደራዊ እርምጃ ይወስዳል፤ በዚህ የተደፋፈረው ሕዝብ በሥርዓቱ ላይ በማመጽ ወያኔን ያስወግዳል፤ ጊዜዓዊ የሽግግር መንግሥትም ይቋቋማል። ሌሎች ሰዎች ደግሞ “እናንተ ከዳር እኛ ከውስጥ እናጣድፈዋለን” ይላሉ። ይህ አባባል ወደ ስትራቴጂ ሲመነዘር የሚከተለውን ይመስላል: ህወሓት ከስልጣን የሚወገደው ሕዝባዊ አመጽና ሕዝባዊ እምቢተኝነት በአንድነት በተግባር ላይ በሚወሉበት ሁለገብ ትግል ነው፤ ዳር አገር ትጥቅ ትግል መሀል አገር ደግሞ ሕዝባዊ እምቢተኝነት፤ ሁለቱን ተደጋግፈው ወያኔን ያስወግዳሉ፤ ጊዜዓዊ የሽግግር መንግሥትም ይቋቋማል። እንዲህ እያልን ከሁለገብ ትግል ብዙ አማራጭ ስትራቴጂዎችን ማሰብ እንችላለን። ከዚህም ሌላ ምን ያህል አመጽ ምን ያህሉስ እንቢተኝነት መደባለቅ ይኖርበታል የሚለው ራሱ ቁጥር ስፍር የሌላቸው አማራጮችን ይዞ የሚመጣ ነው። ከላይ እንደተገለፀው የትግል ስትራቴጂ መረጣ የአንድ ወቅት ሥራ የማይሆነው አዕምሮዓችን በአሠራን መጠን አማራጮችን እያሰፋን የምንመጣ በመሆኑም ጭምር ነው።

ሁለገብ የትግል ስልት ሲባል ሁለቱም ማለትም ሕዝባዊ እምቢተኝነትንና ሕዝባዊ አመጽን አቀናጅቶ መምራት የሚመለከት መሆኑ ግንዛቢ ሊያገኝ ይገባል። በሁለገብ ትግል ውስጥ የገባ ድርጅት በሁለቱም ሜዳዎች መጫወት ይኖርበታል። እኔ ሕዝባዊ እምቢተኝነት ወይም ሕዝባዊ አመጽ ብቻቸውን እንደስትራቴጂ ከተመረጠ የምንፈልገው ቦታ አያደርሱንም፤ ሁለቱ ሲቀናጁ ግን በአንዱ የጎደለው በሌላው ተሟልቶ ስትራቴጂውም የተሟላ ያደርገዋል የሚል እምነት አለኝ።

4. ማጠቃለያ
በዚህ ጽሁፍ ውስጥ “የትግል ስትራቴጂ” እና “የትግል ስትራቴጂ መረጣ” ሲባል እኔ የምረዳውን ለማካፈል ሞክሬዓለሁ። “ሁለገብ ትግል” እንደ ትግል ስትራቴጂ ምን ማለት እንደሆነ እና ለምንስ ለኢትዮጽያ ተመራጭ ነው ብዬ እንደማምን የግሌን አስተያየት አቅርቤዓለሁ። ይህ ጽሁፍ ሁለገብ ትግል ለኢትዮጵያ ይበጃል የምንል ሰዎች ቢያንስ ሳናስብበትና ሳንጨነቅበት በግልብ የወሰነው ጉዳይ አለመሆኑ ያስረዳል ብዬ አደርጋለሁ።

Tadesse Biru Kersmo's photo.
Tadesse Biru Kersmo's photo.
Tadesse Biru Kersmo's photo.

 

The post የትግል ስትራቴጂ ምንነት እና የትግል ስትራቴጂ መረጣ (ክፍል ሶስት: የመጨረሻ) appeared first on Zehabesha Amharic.


አባይን የኦሮሞ ልጆች ልክ አስገቡት –ሙሉነህ ኢዮኤል

$
0
0

MerfeQulef-on-sosial-midia-18012016-300x284ከአዲስ አበባ ማስተር ክራይምና የተቀናጀ የኦሮሚያ ልዩ ዞን የመሬት ቅርምት ጋር በተያያዘ ስሙ በክፉ የሚነሳበት እንደ አባይ ጸሃይ ያለ ሌላ ሰው የለም ቢባል ማጋነን አይሆንም። ይህ ሰው ስምና ግብር ላይገናኙ እንደሚችሉ ጥሩ ማሳያ ነው። ሁለት በጣም ትልቅ ፋይዳ ይላቸውን ነገሮች ይዞ የሚዞር ሰው ነው። አባይና ጸሃይን። አባይም አባይ፤ ጸሃይም ጸሃይ። ይህ ሰው ግን ባለፉት ሁለት አመታት ኦሮሚያ ውስጥ የፈሰስውን የደም ጎርፍ ባሰብን ቁጥር በጆሯችን የሚያቃጭል ስም። የሳጥናኤል ልጅ ነው። መቼም አንረሳውም።

ስለአባይ ሥልጣን

አባይ አማካሪ የሚባል ትግራይ ስሪት ባርኔጣ ጣል አድርጎ ሀይሌ የሚጋል ፈረስ ጋላቢ ነው። ምንም እንኳን ከመለስ ሞት በኋላ ሁላቸውም የተስማሙበትና ሁሉን ያስፈራ አንድ ሰው ከወያኔ መንደር ቢጠፋም እርስ በርሳቸው እየተጠባበቁ አመራር የሚሰጡ ሰዎች ግን አልታጡም። ከቅርብ ጊዜ ወዲህ አባይ ከእነዚህ ሰዎች ውስጥ ድምጹ ከፍ ብሎ የሚሰማ ሰው ሆኗል። በሌላ አገላለጽ የህይለማርያም የቅርብ አለቃ ማለት ነው። እውነተኛው ጠቅላይ ምንስትር።

ጥቂት ቃላት ስለዳንኤል

አባይና ዳንኤል አጭር ቆይታ አድርገው ነበር። ዳንኤል እየተርበተበተ አንድ ጥያቄ ብቻ ጠየቀው። ዳንኤል ሃይለማርያምን ቢሆን የሚጠይቀው እንዲህ አይርበተበትም ነበር። አገሪቷን ከሚገዛው ሰውዬ ጋር እየተነጋገረ እንደሆነ ሲሰማው የደነገጠ ይመስላል። ዳንኤልን ሳውቀው ማንንም የሚፈራ ሰው አልነበረም። በአንድ ወቅት እግዚአብሄር እንደሌለ ሊያስረዳን ፈልጎ ልንረዳለት ባለመቻላችን እንዴት እንደተናደደብን እስከዛሬ አስታውሳለሁ።

አባይና መልሱ

1ኛ የአባይን ስም በክፉ ያነሳ ሁሉ የትግራይን ህዝብ ይጠላል፤

አባይ የኔን ስም በክፉ የሚያንሱ ሁሉ የትግራይን ህዝብ የሚጠሉ ናቸው አለን። አባይ በዚህ አባባሉ “እኔና የትግራይ ህዝብ አንድ ነን” እያለን ነው። እውነት አባይና የትግራይ ህዝብ አንድ ናቸው? አባይ የኦሮሞን ህዝብ በጣም እንደሚጠላ በመቶዎች እያስገደለ፣ በሽዎች እያቆሰለና እያሳሰረ አረጋግጦልናል። በተጨማሪም አጋጣሚውን ተጠቅሞ ሃዘኑን ለመግለጽ ባለመሞከር ለፈሰሰው ደም ቅንጣት ሃዘን እንደሌለው አሳይቷል። ይህ ሁሉ የሚያሳየው አባይ ኦሮሞን እንደሚጠላ ነው። ስለዚህ አባይና የትግራይ ህዝብ አንድ ከሆኑ የትግራይ ህዝብም ኦሮሞን አጥብቆ ይጠላል ማለት ነው። እውነት የትግራይ ህዝብ ልክ እንደአባይ የኦሮሞን ህዝብ ይጠላል? ለዚህ ጥያቄ መልስ መመለስ ያለበት የትግራይ ህዝብ ብቻ ነው። መልሱን ከትግራይ ህዝብ እጠብቃለሁ።

2ኛ የአባይ ሽንፈት

አባይ ማስተር ክራይሙን የሚቃወም ልክ ይገባል ብሎ ነበር። ይህን ማለቱን የሚገልጽ የድምጽ ማስረጃ ኦኤምኤን አቅርቧል። ስለዚህ ጉዳይ ምን ትላለህ ሲባል አባይ የሰጠው መልስ እጅግ አስገራሚ ነው። “ከሳሾቼ ያቀረቡት ፓረግራፍ የኔ አይደለም” የሚል። ለማስረጃ የቀረበበት ድምጹ ሆኖ እያለ ጽሁፉ የኔ አይደለም ማለቱ ሰውዬው ከራሱ ድምጽ እየሸሸ እንደሆነ ነው። ድምጹ የኔ አይደለም ማለት አልቻለም። ይህ ማለት ደግሞ አባይ የራሱ ድምጽ አሳፍሮታል ማለት ነው። ይህ የሚያሳየው አባይ ከራሱ ከድምጽ እየሸሸ እንደሆነ ነው። ይህ ማለት ደግሞ የመሸነፍ ምልክት ነው። ይህ ማለት ደግሞ አባይ ልክ ገባ ማለት ነው።

 

The post አባይን የኦሮሞ ልጆች ልክ አስገቡት – ሙሉነህ ኢዮኤል appeared first on Zehabesha Amharic.

“አዲስ አበባ የፌዴራልም፤ የኦሮሚያም ከተማ ሆና መቆየት አለባት።” –ሌንጮ ባቲ |የድምጽ ቃለምልልስ

መምህር ብሩክ ገብረ ሊባኖስ ስለ በዓለ ጥምቀት ትርጓሜና አከባበር ይናገራሉ

ሃገርና ቅርስ ሽያጩ ይቁም!! –በኢየሩሳሌም የሚገኘዉ ንግሥት ዘዉዲቱ ህንፃ

$
0
0

በኢየሩሳሌም የሚገኘዉ ንግሥት ዘዉዲቱ ህንፃ

Jerusalem123 -satenawሃገር ቅርስ ነዉ ቅርስ ሃገር ነዉ፡፡ ቅርስ ሲሸጭ አገር እና ማንነት አብሮ ይሸጣል፡፡ ቀደምት አባቶቻችን ለዚህ ትዉልድ ብዙ ታሪካዊ ቅርሶችን አዉርሰዉን አልፈዋል፡፡ ይህን አኩሪ ታሪክ እና ቅርስ የተረከብን ትዉልዶች በዚህ ዘመን ከማህጸኗ ለወጡ የእንግዲህ ልጆች የአገራችንን ቅርስና ክብር አሳልፈን በመስጠታችን  የአገራችን ህልዉና በከፍተኛ አደጋ ላይ ወድቋል፡፡ ይህ ከአንድ ጎጥ የተፈለፈለ የማፍያ ቡድን ከባዕዳን ጋር በመመሳጠር የኢትዮጵያን የረዥም ታሪክ እና ዓለም አቀፋዊ ክብር በማጥፋት ይኸዉ ለ25 ቆይቷል፡፡ በአገር ዉስጥና እጁ በሚደርስበት ሥፍራ ሁሉ ኢትዮጵያን እና ኢትዮጵያዉነትን በማጥፋት ዘመቻ ላይ ተጠምዶ ይገኛል፡፡ ይኸዉም ኢትዮጵያ በረዥም ጊዜ ታሪካዊ ትስስር ካላቸዉ  አገሮች አንዷ እስራኤል ነች፡፡ ይህች አገር የዓለማችን የፖለቲካ እና የሃይማኖት እንብርት ነች፡፡ ከእስራኤል የሚነሳ ነፋስ በሁሉም አገር በቀጥታ ሆነ በተዘዋዋሪ ሁሉንም ያነቃንቃል፡፡  ለዚህም ቀደምት ኢትዮጵያዉያን ነገስታትና የነገስታቱ ቤተሰቦች በተለያዬ መንገድ አገራቸዉን የሚያስጠራና የሚያኮራ ቅርስ በዚች የዓለም እንብርት ጥለዉልን አልፈዋል፡፡

ከነዚህም በንግሥተ ሳባ፣ አጼ ዮሐንስ ፣አፄ ሚኒሊክ፣ንግስት ጣይቱ፣ንግስት ዘዉዲቱ፣ አፄ ሃይለስላሴ እና ብዙ የነገስታቱ ቤተሰቦች በኢየሩሳሌም ለሚገኘዉ የኢትዮጵያ ገዳም ያወረሱትና በከፊል በመንግሥት ደረጃ የሚተዳደሩ ጥንታዊ ቦታዎችና ቅርሶችን ጥለዉልን አልፈዋል፡፡  ከነዚህ ቅርሶች መካከል የኢትዮጵያ ህዝብ ባላወቀዉ መልኩ የተሸጡ አሉ አሁንም በስፋት ለመሸጥ የተዘጋጁ እንዳሉ ፍንጮች እየወጡ ነዉ፡፡ ለዚህም ለማስረጃ ያክል የአጼ ሃይለስላሴ በጣሊያን ወረራ ጊዜ ወደ እንግሊዝ ከመሄዳቸዉ በፊት አርፈዉበት የቆዩበትን ቤትና ቦታ የንጉሳያኑ ቤተሰብና የኢትዮጵያ መንግሥት  የይገባኛል ክርክር ለብዙ ዓመታት ሲካሄድ ቆይቶ በንጉሳዉያኑ ቤተሰብ አሸናፊነት ሲጠናቀቅ የንጉሳያኑ ቤተሰብ  1.5 ሚሊዮን ዶላር ለባእዳን  አሳልፈዉ ሽጠዉታል፡፡ በዚህም ምክንያት ከ30 ዓመታት በኢየሩሳሌም ምእመናን ማህበር በተሰባሰቡ ኢትዮጵያዉያን የተገዛ ቤት እና የብዙ ኢትዮጵያን በሐዘንና በማህበራዊ ጉዳዮች የሚገናኙበት ቤትም ያለምንም ካሳ ተወስዷል፡፡

የንጉሳዉያኑ ጠበቃ የነበረዉ በተዘዋዋሪ እራሱ ህንጻዉን ከገዛ በኋላ በአሁኑ ወቅት ይህን ቦታ በ11 ሚሊዮን ዶላር ለሽያጭ አቅርቦት ይገኛል፡፡ የዚህ ቦታ ያለአግባብ በመሄዱ በምንቆጭበት ስዓት የኢትዮጵያ መንግሥት በአንባሳደር ህላዌ እና በገዳሙ ዉስጥ በተሰገሰጉ የህዋት መነኮሳት ጋር በመመሳጠር በ1928 እንደ አዉሮፓ አቆጣጠር የታነጸዉን የእቴጌ ዘዉዲቱ ህንፃ ንግስቲቱ በዘመኑ በኢየሩሳሌም ይኖሩ ለነበሩ ቅዱሳን አባቶች ድጋፍ ይሆን ዘንድ ከህንጻዉ ከሚገኘዉ ኪራይ ሲሶዉን እንዲተዳደሩበት ለኢትዮጵያዉያን በቅርስነት ያስረከቡትን ህንጻ በእድሳት ስም በብዙ ሚሊዮን ዶላር በሚስጢር በመሸጥ ለገዥዎቹ ለማስረከብ ዝግጅቱ ተጠናቋል፡፡ ቀደም ሲል ወያኔ ይህን ታሪካዊ ህንፃ ለመሸጥ በተደጋጋሚ ለገዳሙ ጥያቄ ያቀረበ ቢሆንም በወቀቱ በነበሩ አባቶች ጥንካሬ እየተከላከሉ እስካሁን ደርሷል፡፡

የህወሀት መንግሥት ይህን ለማድረግ ለምን ፈለገ ለሚለዉ ቅርሱ በኢትዮጵያዉያን የቆመ እና ኢትዮጵያን የሚወክል በመሆኑ ይህን ማጥፋት የግድ ስለሚለዉ ብቻ ነዉ፡፡ ሁሉም ነገር በራሱ ዘዉግ ብቻ የቆመ እና በራሱ ዘዉግ እንዲኖር የሚፈልግ ጠባብና ስግብግብ ቡድን እንጂ የኢትዮጵያዊነት መንፈስ የሌለዉ በመሆኑም ጭምር ነዉ፡፡ ይህን ከዳር ለማድረስ የራሱን ዓላማ አስፈጻሚ መነኮሳት በገዳሙ ዉስጥ እና ከዉጭ ሌሎች ኃላፊነት የጎደላቸዉን ሰዎች በማደራጀት የቅርስ ሽያጭ ዓላማዉን ለማስፈጸም ከመጨረሻዉ ደረጃ ላይ ደርሷል፡፡ ህወሃት በአገር ዉስጥ እና በአገር ዉጭ ሃገርንና ቅርስን እንዲሁም ህዝብን  በማጥፋት ተግባር  ላይ ተጠምዶ  ይገኛል ለዚህም በአሁኑ ስዓት በኦሮሞ እና በአማራ ህዝብ ላይ እየፈጸመ ያለዉን መመልከት በቂ ነዉ፡፡ ስለዚህ ኢትዮጵያዉያን ዘርና ሃይማኖት ሳይለየን አገርንና ቅርሳችንን ከህወሃት ጥፋት ለማዳን ሁሉም በአንድነት መነሳት እንዳለበት ሊታመን ይገባል ለዚህም፡-

1/ አባቶቻችን እና እናቶቻችን ደም እና አጥንት ገብረዉ ያስረከቡንን ቅርስ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን የመጠበቅና ጠብቆም ለትዉልድ የማስረከብ ኃላፊነት እንዳለባት በመረዳት የበኩሏን ድርሻ መወጣት ይገባታል፡፡ ይኸዉም አብዛኛዎቹ ቅርሶች በቤተ ክርስቲያኗ ስም ስለሚገኙ እና በመነኮሳት ስም በዘርና በጎጥ ተደራጅተዉ በገዳሙ ላይ እና በቅርሱ ላይ እያደረሱ ያሉት ጥፋት ከፍተኛ እንደሆነ በመንበሩ ላይ የተቀመጡት አቡነ ማቲያስ በሚገባ የሚያዉቁት በመሆኑ የተሸከሙትን ሃላፊነታቸዉን በመዘንጋት ለሚደርሰዉ ጥፋት ታሪክ ይቅር የማይለዉ እና ለዚህ ቅርስ መጠበቅ ብለዉ ህይወታቸዉን ባጠፉት አባቶች ነፍስ በእግዚአብሔርም የሚያስጠይቅ መሆኑን መረዳት ይገባል “ፈሪሃ እግዚአብሔር እና ዕምነት ካለ ?”፡፡

2/  በእስራኤል የሚገኙ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች እና ቤተ እስራኤላዉያን በአንድ በመተባበር በጉዳዩ ላይ ግልጽ ማብራሪያ  ከሚመለከታቸዉ አካላት መጠየቅ የደረሱበትን ለህዝብ ማሳወቅ ግድ ይላቸዋል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ እራሳቸዉን በማደራጀት በእስራኤል የሚገኙ የኢትዮጵያዉያን ቅርሶች በዝርዝር መያዝ እና ለወደፊት ህገወጥ ሽያጭ እንዳይካሄድ በህግ የሚታገድበትን መንገድ ማፈላለግ ተቀዳሚ ተግባራቸዉ ሊሆን ይገባል፡፡

3/ በመላዉ ዓለም የሚገኙ ኢትዮጵያዉያን እና ትዉልደ ኢትዮጵያዉያን በተለይ የኢትዮጵያ ቅርስና ባለአደራ ጠባቂ እንዲሁም ሌሎች መንግስታዊ  ያልሆኑ ድርጅቶች እራሳቸዉን በማቀናጀት በእስራኤል የሚገኙ የኢትዮጵያዉያን ቅርሶች የሚጠበቁበትን መንገድ ማመቻቸት እና አሁን ለሽያጭ በቀረበዉ የንግስት ዘዉዲቱ ህንጻ ላይ ተቃዉሟቸዉን ለእስራኤል መንግስት ማሳወቅ አስፈላጊ ነዉ፡፡

እግዚአብሔር ኢትዮጵያን ይጠብቅ!!

ጽናት ዘላለም

The post ሃገርና ቅርስ ሽያጩ ይቁም!! – በኢየሩሳሌም የሚገኘዉ ንግሥት ዘዉዲቱ ህንፃ appeared first on Zehabesha Amharic.

Hiber Radio: በኦሮሚያ ክልል ተቃውሞው ተጠናክሮ ቀጥሏል፣ ዶ/ር መረራ ጉዲና ሕዝቡ ጥያቄ ስላልተመለሰ ትግሉ ይቀጥላል ብለዋል፣ አገዛዙ ሙስሊሙና ክርስቲያኑን ለማጋጨት አዲስ ዶክመንተሪ ፊልም አውጥቶ የሙስሊሙን ሰላማዊ እንቅስቃሴ ከሽብር ጋር አመሳሰለ፣ አልሽባብ በኢትዮ ኬነያ ድንበር ላይ በርካታ ወታደሮችን መግደሉን እና መማረኩን ገለጸ

$
0
0

Hibir Radio Cover
የህብር ሬዲዮ ጥር 8 ቀን 2008 ፕሮግራም

<...> ጋዜጠኛ ሳዲቅ አህመድ > ስለተሰኘው የአገዛዙ ዶክመንተሪ አስመልክቶ ከሰጠን ቃለ መጠይቅ የተወሰደ (ሙሉውን ያዳምጡት)
በሎስ አንጀለስ የጥምቀት በዓል አከባበር(ቆይታ ከጋዜጠኛ ነጻነት ሰለሞን ጋር)

በዘንድሮ ታክስ አሰራርና የሕክምናና ለበጎ አድራጎት ወጪ የሆኑትን በተመለከተ ሊወሰዱ የሚገባቸው ጥንቃቄዎች (ውይይት ከአትላንታ ከአቶ ተካ ከለለ የቲኬ ሾው አዘጋጅ ጋር ሙሉውን ያዳምጡት)

<...> ዶ/ር መረራ ጉዲና የኦህዴድን ማስተር ፕላኑ ቀርቷልና የቀጠለውን ተቃውሞ በተመለከተ ወቅታዊ ሁኔታ ላይ ከአገር ቤት ከሰጡን ቃለ መጠይቅ የተወሰደ (ሙሉውን ያዳምጡት)

የአሜሪካው ፕ/ት ባራክ ኦባማ የመጨረሻቸው በሆነው በዓመታዊ ንግግራቸው ላይ ያሰሟቸው ታሪካዊ ንግግራቸው እና የቀረቡባቸው ትችቶች (ልዩ ዘገባ)
ሌሎችም

ዜናዎቻችን
አወዛጋቢውን የኢትዮጵያና የሱዳን ድንበር በዚህ ወር እንዲያካልሉ ለውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች መመሪያ ተሰጠ
በኦሮሚያ ክልል ተቃውሞው ተጠናክሮ ቀጥሏል

ዶ/ር መረራ ጉዲና ሕዝቡ ጥያቄ ስላልተመለሰ ትግሉ ይቀጥላል ብለዋል

የአቶ አንዳረጋቸው ጽጌ የጤንነት ሁኔታ አሳሳቤ እየሆነ መምጣቱን አንድ ታዋቂ እንግሊዛዊ የጤና ባለሙያ አሳሰቡ
“አንዳርቸው ጽጌ ባስቸኳይ ካልተለቀቁ ጤንነታቸው ዳግም ወደ ማይመለስበት ሁኔታ ሊሸጋገር ይችላል”ዶ/ር ቤንጃሚን

በኢትዮጵያ ውስጥ የተከሰተው ረሃብ የአለማቀፉ የግብርና ተቋምን በእጅጉ አሳስቦታል

በቅሊንጦ ማረሚያ ቤት ባልታወቀ ሁኔታ የሞተው ወጣት ስርዓተ ቀብር ተፈጸመ

አገዛዙ ሙስሊሙና ክርስቲያኑን ለማጋጨት አዲስ ዶክመንተሪ ፊልም አውጥቶ የሙስሊሙን ሰላማዊ እንቅስቃሴ ከሽብር ጋር አመሳሰለ

መምህር ግርማ ወንድሙ ከእስር ከተፈቱ በሁዋላ ተከታዮቻቸውን አመሰገኑ

አልሽባብ በኢትዮ ኬነያ ድንበር ላይ በርካታ ወታደሮችን መግደሉን እና መማረኩን ገለጸ

ኬኔያ በሽብር ቡድኑ ላይ አይቀጡ ቅጣት እርምጃ እንደምትወስድ አስታወቀች

The post Hiber Radio: በኦሮሚያ ክልል ተቃውሞው ተጠናክሮ ቀጥሏል፣ ዶ/ር መረራ ጉዲና ሕዝቡ ጥያቄ ስላልተመለሰ ትግሉ ይቀጥላል ብለዋል፣ አገዛዙ ሙስሊሙና ክርስቲያኑን ለማጋጨት አዲስ ዶክመንተሪ ፊልም አውጥቶ የሙስሊሙን ሰላማዊ እንቅስቃሴ ከሽብር ጋር አመሳሰለ፣ አልሽባብ በኢትዮ ኬነያ ድንበር ላይ በርካታ ወታደሮችን መግደሉን እና መማረኩን ገለጸ appeared first on Zehabesha Amharic.

ፍካሬ ዜና:- በአፍሪካ ቀንድ እየታየ ያለው የኃይል አሰላለፍ ወያኔን እያራደው መሆኑ ታወቀ |የካራቱሪ ስራ አሲካያጅ በአለም አቀፍ ደረጃ የውሳኔ ማገጃ አገኘሁ አለ

$
0
0

UN-Land-Grab-Report

ርዕስ አንቀጽ

ፍካሬ ዜና

ጥር 8 ቀን 2008 ዓም

– – – – – – – – – -

አጫጭር ዜናዎች
– በወያኔ አግአዚ ጦር የተገደሉት ከ140 መብለጡ ተነገረ
– ግብርና ሌላም ፈጽመዋል የተባሉ ተከሰሱ
– የቦምብ አደጋ ጉዳት
በአፍሪካ ቀንድ እየታየ ያለው የኃይል አሰላለፍ ወያኔን እያራደው መሆኑ ታወቀ፡፡
ወያኔ በየትምህርት ተቋም የደህንነት ሠራተኞችን መመደቡ ታወቀ፡፡
የካራቱሪ ስራ አሲካያጅ በአለም አቀፍ ደረጃ የውሳኔ ማገጃ አገኘሁ አለ
የሳዑዲ አረቢያ መንግስት አንዲት ኢትዮጵያዊትን አንገቷን በሰይፍ በመግጣት የግድያ ቅጣት ፈጸመባት በቱርክ፤ በኢራክና በኢንዶኖዢያ በቦምብ አደጋ ሰዎች ሞቱ
አልሸባብ የአፍሪካ ህብረት የሰላም አስከባሪ ኃይል የጦር ሰፈርን አጥቅቶ 60 ወታደሮች ገደልኩ አለ

ወያኔ የተነሳውን ሕዝባዊ ቁጣ አብርጅያለሁ፤ የአዲስ አበባን መስፋፋትም ዕቅድ ሰርዥላሁ ቢልም ሕዝባዊ አመጽ መቀጠልን በየቀኑ ከሚደርሱ መረጃዎች ማወቅ ያቻላል ሲል ታዛቢዎች ጠቁመዋል ። በያዝነው አላቂ ሳምንት ወያኔ በነቅምቴ፤ አምቦ፤ ሱሉልታ፤ ሐረርጌ፤ ጎንደር፤ባህር ዳር፤ ጅማ፤ ወሊሶና ወልቂጤ ከ 185 ዜጎች በላይ ለእስር መዳረጉ ታውቋል ። በባሀር ዳር ያፈሳችውን ወደ ጎንደር እስር ቤት ለምን እንደሚወስድ ግን የታወቀ የለም ። ተቃውሞው እየቀጠለ ነው ። ሆኖም አማራን መግደል ስምሪታችን ነው የሚሉ ጠባቦችና አሁን መድረኩን ሊያጣብቡ የሚጥሩ ግለሰቦች ያለውን ትግል የክልል አጥር ሰርተው ሊገልጹት መጣራቸው የሚያስከትለው ሽንፈት ግልጽ ቢሆንም እስካሁን ግን ትግሉ በመፋፋም ላይ ነው እንጂ አልበረደም ።

ወያኔ የኢሕአፓ ስም ያለፈውን አንስቶ ከማውገዝና ከመክሰሰ ባሻገር በምንም መንገድ እንዳይነሳ ያለው አቅዋሙ አሁንም ታድሶ እየቀጠለ መሆኑን ውስጠ አዋቂዎች አጋልጠዋል ። ወያኔ ፍኖተ ዴሞክራሲን ራዲዮን ለመዝጋት/ለማፈን ዛሬም ቢጥርም በዚሁ ራዲዮ የሚነሱትን ክሶችና ቁም ነገሮች መልስ ሊሰጥ ሳያቃጣ ዓመታት

አልፈዋል ። ይህ አቅዋም ይቀየርና ህዝብ ለሚያደምጠው ለፍኖተና ኢሕ አፓ ምላሽ እንሥጥ ያሉ የወያኔ ለፋፊዎች አርፋችሁ ተቀመጡ፤የኢሕአፓን ስም አታንሱ መባላቸው ሊታወቅ ተችሏልም ተብሏል ።

  •   በወያኔ መከላካያ ውስጥ የኦሮሞ ተወላጅ የሆኑ ከፍተኛ ወታደራዊ መኮንኖችን ለማሰር ሴራ እየተጠነሰሰ መሆኑን ውስጠ አዋቂ ምንጮች አጋለጡ። በየቦታዊ እየተካሄደ በሚገኘው ሕዝባዊ የተቃውሞ እንቅስቃሴ ላይ እየተወሰደ ያለው የሃይል እርምጃ ከመጠንና ከገደብ ያለፈ ነው በማለት ጥያቄ ያነሱ በርከት ያሉ መኮንኖች እንዳሉ ሲታወቅ ከእነዚህ መኮንኖች ውስጥ አንዳንዶቹን ቃሊቲ ከሚገኘው ሎጅስቲክ መምሪያ ናዝሬት ወደ ሚገኘው የሎጂስቲክ መምሪያ እንዲዛወሩ የተደረገ መሆኑ ታውቋል። ከመከላከያ ውስጥ በተገኘው መረጃ መሰረት በቀጣይ ግምገማ ጠንካራ ተቃዋሚዎች የሆኑት እየተለቀሙ ከማእረግ መግፈፍ እሰከማሰር ድረስ በሚዘልቅ እርምጃ በመውሰድ ለመቅጣት የታቀደ መሆኑ ታውቋል። በሌላ በኩል ደግሞ ወያኔ አመጹን በማፈን በኩል ከፍተኛ ሚና ለነበራቸውና ወደ ሌሎች ቦታዎች ቢዛመት ተገቢ መካለክል ሊያደርጉ ይችላሉ ተብለው ለታመነባቸው መኮንኖች ከፍተኛ የማዕረግ እድገት ሊሰጥ የተዘጋጀ መሆኑ ተዘግቧል።
  •   ወያኔ በሻዕቢያ ላይ ክሱን ሲደረድር የጅቡቲን ጨቋኝ አገዛዝ የሚቃወመውን የአፋሮች የፍሩድ ተቃዋሚ እንቅስቃሴንም በኤርትራ የሚረዳ ብሎ ከሷል ። የፍሩድ ድርጅት ግን ይህን በማስተባበል ወያኔ ለጨቁኙ የጅቡቲ ኦማር ገሌህ ሙሉ ድጋፍን እየሰጠች መሆኗን አጋልጧል ። የጅቡቲ አገዛዝ ባለፈው ታህሳስ በርክታ ዜጎቹን ከመግደሉ ባሻገር አፈናውን በመቀጠል ብዙ ተቃዋሚዎችና የሰብዓዊ መብት ተቋሚዎችን እያሰረ መሆኑ ታውቋል ። የጅቡቲ አገዛዝ ወያኔን ለመደገፍ ሲል ኢትዮጵያዊ ስደተኞች ላይ በደል እንደሚፈጽምም ተጋልጧል ። ሱዳንም ብትሆን በወያኔ ደጋፊነቷ ስደተኞችን እያሰቃየች መሆንዋ መረሳት የለበትም ።
  •   በሶማሊያ በአሜሪካ ገፋፊነት ጣልቃ የገቡት የአፍሪካ ጦሮች ጉዳት እየደረሰባቸው መሆኑ ተዘግቧል ። በዚህ በያዝነው ሳምነት በሳውዲ አረቢያ፤ካታርና ግብጽ የሚደገፈው አሸባሪው የአል ሻባብ ቡድን ስድሳ የኬንያ ወታደሮችን መግደሉን አስታውቋል ። ወያኔም ባይናገርም እየደረሰብት ያለው ጥቃት ቀላል እይደለም ። ሶማልያ የገቡት የአፍሪካ ጦሮች ራሳቸው መሳሪያን ጥይት ለአል ሸባብ መሳሪያን ጥይት እየሸጡ መሆኑም መጋለጡ የሚታወስ ነው ።

    የወያኔ አግአዚ ጦር ከ140 የሚበልጡ ኢትዮጵያውያንን ገደሉ በማለት የሰብአዊ መብት ድርጅቶች አጋለጡ

    በዚህ ሳምንት ግሎባል ቮይስ ኦን ላይን የተባለው ድርጅት በቅርቡ በወያኔ አግአዚ ወታደሮች የተገደሉት ዜጎች ቁጥር ከ140 በላይ መሆኑን ሂውማን ራይትስ ዎች የተባለውን ድርጅት ዋቢ በማድረግ ጠቅሶ ከእነዚህ ውስጥ ቢያንስ 10 የሚሆኑት በእስር ቤት በስየል ምርመራ (ቶርቸር) የሞቱ መሆናቸውን የሚገልጽ መረጃ ያገኘ መሆኑን ዘግቧል። ከሞቱት ውስጥ

የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች፤ ሴቶች አርሶ አደሮች እና መምህራን የሚገኙበት መሆኑን ዘግቦ 70 ከመቶ የሚሆኑት ወንዶች መሆናቸውን ጠቅሷል። አንዲት የሰባት ወር እርጉዝ ሴት ከእህቷ ጋር ከአደጋው ለማምለጥ ሲሸሹ መገደላቸው መረጃ የደረሰው መሆኑን በመግለጽ ድርጅቱ ባወጣው ዘገባው ላይ ዘርዝሯል። በተያያዘ ዜና የሕዝቡ አመጽና እንቅስቃሴ ለስልጣኑ አስጊ መሆኑን የተረዳው ወያኔ በዚህ ሳምንት በአገልጋዩ በኦህዴድ አማካነይነት በዜና ማሰራጫዎች ባሰራጨው መግለጫ የአዲስ አበባ ማስተር ፕላን ሙሉ በሙሉ የተሰረዘ መሆኑን ገልጿል። የኦህዴድ ማእከላዊ ኮሚቴ በአዳማ/ናዝሬት ባካሄደው የሶስት ቀን ስብሰባ ሰፊ ውይይት አካሂዶ የማስተር ፕላኑ እቅድ እንዲስረዝ ውሳኔ አስተላልፏል ተብሏል። ይሁን እንጅ በተለያዩ ቦታዎች እየተካሄዱ ያሉት አመጾች ከመግለጫው በኋላ ተጠናክረው ቀጥለዋል። በጅማ በሃረርጌ ክፍል ሃገር እና በሌሎች ቦታዎች ተማሪዎች የሚያካሂዱትን የተቃውሞ እንቅስቃሴ ተስፋፍተው እንደቀጠሉ ተዘግቧል።

ግብርና ሌላም ማጭበርበር ፈጽመዋል የተባሉ ተከሰሱ፡፡

የወያኔ ከፍተኛ ባለስልጣናት በከፍተኛ የንግድ ድርጅቶች ውስጥ የባለቤትነት ድርሻ እንዳላቸው አገር የሚያውቀው ነው፡፡ እነዚህ ድርጅቶች ከውጪ ወደ አገር ውስጥ እቃ ሲያስገቡም ሆነ ወደ ውጪ ሲልኩ ከቀረጥ ነጻ ናቸው፡፡ ሌላው ቀርቶ የጉምሩክ የመጋዘን ኪራይ እንኳ አይከፍሉም፡፡ ግብር ያለ መክፈል መብት አላቸው፡፡ ከእነዚህ የንግድ ኩባንያዎች ጀርባ ያሉት እነ አዜብ ጎላ፣ በረከት ስምኦን፣ ስብሀት ነጋ፣ ስዩም መስፍን፣ አዲሱ ለገሠ፣ አባዱላ ገመዳ፣ ሳሞራ ዩኑስ፣ ወዘተ. በመሆናቸው ቀረጥ አይነካቸውም፡፡ ይህ ሁኔታ ከወያኔ ውስጣዊ የፖለቲካ ሽኩቻ ጋር በቀጥታ እንደሚያያዝ የሚያሳዩ ምልክቶች አሉ፡፡ ከአንድ የንግድ ድርጅት ጀርባ ባለሀብት የሆነው የወያኔ ቁንጮ ተቀባይነቱ ሲመናመን የዚያን ጊዜ የንግድ ድርጅቱ ላይ አደጋ ማንዣበብ ይጀምራል፡፡ ከእነዚህ ድርጅቶች ውስጥ በቅርቡ ክስ የተሰረተባቸው “የሀሮን ኮምፒዩተር

የንግድ ድርጅት” እና “አክሰስ ሪል ስቴት” የተሰኙ ድርጅቶች ናቸው፡፡ ሀሮን የተሰኘው ድርጅት ከአገር ውስጥ ገቢ መሥሪያ ቤት በተሰጠው ፍቃድ የሽያጭ ማሽኖችን ከውጪ እያስገባ የሚያሰራጭ ድርጅት ሲሆን የተከሰሰው ከ200 ሚሊዮን ብር

በላይ የግብር ማጭበርበር ፈጽሟል በሚል ነው፡፡ እንዲህ ያለ ወንጀል በአንድ ቅጽበት የሚከሰት ሳይሆን በሂደት የሚፈጸም መሆኑን የሚያስረዱ ለጉዳዩ ቅርበት ያላቸው ወገኖች እንደሚሉት ከሀሮን ጋር ይሰሩ የነበሩ የወያኔ ቁንጮዎችን ችግር ላይ መውደቃቸውን የሚያሳይ መሆኑን ያስረዳሉ፡፡ በተመሳሳይ መልኩም የአክሰስ ሪል ስቴት አክሲዮን ማህበር የቦርድ ሰብሳቢ የነበሩት አቶ ኤርምያስ አመልጋ ከደምበኞች የተቀበሉትን 1.4 ቢሊዪን ብር ያደረሱበት ባለመታወቁ ጥር 2 ቀን 2008

ዓ.ም. ታስረዋል፡፡ አቶ ኤርምስ ከዚህ ወንጀል ሸሽተው ከአገር ኮብልለው እንደነበር ይታወሳል፡፡ ከአቶ ኤርሚያስ ጋር ይሠራሉ ከሚባሉት ውስጥ የሟቹ የመለስ ዜናዊ ሚስት አዜብ ጎላ አንዷ እንደሆነች ይነገራል፡፡ እነዚህን ሁኔታዎች በቅጡ ያስተዋሉ የፖለቲካ ተንታኞች እንደሚሉት እንዲህ ያሉ ሁኔታዎች እየሰፉ በሄዱ ቁጥር የወያኔን የእርስ በእርስ ሽኩቻ እንደሚያጦዙትና የወያኔን ሥርዐት ሊንዱት እንደሚችሉ ነው፡፡

የቦምብ አደጋ ጉዳት አደረሰ

ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ቦምብ እንደ ድንጋይ እየተወረወረ የዜጎችን ህይወት እየቀጠፈና አካላዊ ጉዳት እያደረሰ መሆኑ ታወቃል፡፡ ጥር 1 ቀን 2008 ዓ.ም. በጂማ ዩኒቨርሲቲ ኪቶ ፉርዲሳ ካምፓስ ከምሽቱ አራት ሰዓት አካባቢ ቦምብ ተወርውሮ

በተማሪዎች ላይ የአካል አደጋ አድርሷል፡፡ ከሳምንት በፊት በዲላ ዩኒቭርሲቲ ሦስት ቦምቦች ተወርውረው የተማሪዎችን ሕይወት ከማጥፋታቸውም በላይ በርካታ ተማሪዎች ላይ ከባድና ቀላል የአካል ጉዳት ማድረሳቸው መዘገቡ ይታወሳል፡፡ በተመሳሳይ ሁኔታም በአንዋር መስጊድ በተወረወረ ቦምብ የአካል ጉዳ መድርሱ ይታወሳል፡፡ ከሕዝብ የተገኘው አስተያየት እንደሚያስረዳው እንዲህ ያለው ድርጊት የወያኔ እንጂ የሌላ የማንም ሊሆን እንደማይችል ነው፡፡ ወያኔ የመንግስትን መዋቅር የሚጠቀም አረመኔ አሸባሪ ቡድን በመሆኑ ሕዝባዊ አመጽ እየጎለበተ በሄደ ቁጥር እንዲህ ዓይነቱን የሽብር ተግባር ሊፈጽም እንደሚችል የማያጠራጥር እንደሆነ ብዙዎች ያስረዳሉ፡፡ወያኔ ሕዝብን የሚከፋፍል ጥቃቶችን ሊያደርስ ዝግጂ መሆኑ ማንም መሳት የለበትም ሲሉ ታዛቢዎች አሳስበዋል ።

በአፍሪካ ቀንድ እየታየ ያለው የኃይል አሰላለፍ ወያኔን እያራደው መሆኑ ታወቀ፡፡

ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ በሳዑዲ አረቢያ መሪነት ኩየትና ኳታርን ጨምሮ በየመን የሚንቀሳቀሱትን የሁቲ አማጽያንን ለመምታት በኤርትራ የመሰረቱት ወታደራዊ አንቅስቃሴ ለወያኔ ትልቅ ስጋት እንደሆ ለማወቅ ተችሏል፡፡ ይህን ሁኔታ የአካባቢው የፖለቲካ ተንታኞች በሁለት መልኩ ያስቀምጡታል፡፡ አንድ ይህ ከኤርትራ ጋር እየተደረገ ያለው ወታደራዊ እንቅስቃሴ ግብፅ ከዓባይ ግድብ ጋር በተያያዘ በየጊዜው ለምታሰማው ዛቻ መሳርያ ሊሆናት እንደሚችል አያጠራጥርም፡፡ ሁለት ኤርትራ ወታደራዊና ኤኮኖሚያዊ አቅሟን መገባት ይስችላታል፡፡ የፖለቲካ ተንታኞቹ እንደሚሉት ይህ በየመን ስም እየተደረገ ያለው ወታደራዊ እንቅስቃሴ ዋናው ግቡ የዓባይ ግድብ መሆኑን መገመት ስህተት አይሆንም ፡፡ እዚህ ላይ መታወስ ያለበት ኢራን አሰብን በግል ሀብትነት ከያዘችው አመታት መቆጠራቸው ነው፡፡ ይህ ደግሞ ሁኔታውን ያወሳስበዋል፡ ፡ በሌላ አንጻር ደግሞ የወያኔ የጡት እናት የሆነችው ቻይና በጅቡቲ የባህር ኃይሏን አስፍራለች፡፡ ሌላዋ የወያኔ አጋር አሜሪካ በአርባ ምንጭ የነበራትን የሰው-አልባ ተዋጊ ጄት ማረፊያ ጣቢያ በቅርቡ ዘግታ መውጣቷ ወያኔዎቹን እንደረበሻቸው ቢታወቅም ከአሜሪካ ጋር ያላቸውን ግንኙነት እንደማያላለው የሚናገሩ የፖለቲካ ተንታኞች ቁጥር ባርካታ ነው፡፡ የወያኔ ስጋት የሆነው የሻቢያ ከዓረብ አገራት ጋር ያለው ግንኙነት እየጠነከረ መሄዱና የኤርትራ መሬት ለዓረቦች የወታደራዊ ልምምድ ማድረጊያነት መዋሉ ወያኔን እንቅልፍ እንደነሳው ውስጥ አዋቂዎች ያስረዳሉ፡፡

ወያኔ በየትምህርት ተቋም የደህንነት ሠራተኞችን መመደቡ ታወቀ፡፡

ከዚህ ቀደም ከነበረው በተለይ የወያኔ ደህንነቶች በትምህርት ተቋማት ቅጥር ጊቢና አካባቢው በብዛት እየታዩ መሆኑን ተማሪዎችና መምህራን በስጋት ይናገራሉ፡፡ እነዚህ የደህንነት ሠራተኞች እንደተማሪ በመልበስ የተማዎችን እንቅስቃሴ በቅርበት በመከታተል የእራሳቸውን እርምጃ እንዲወስዱ ማለትም ተኩሰው መግደል እንደሚችሉ ሥልጣን እንደተሰጣቸው ሾልኮ የወጣው መረጃ ያስረዳል፡፡ እነዚህ የደህንነት ሠራተኞች የተመደቡት በዩኒቭርሲቲዎች፣ ኮሌጆች፣ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤቶችና ሌሎት የትምህርት ሥልጠና ተቋማት ግቢ ውስጥና ከግቢ ውጪ መሆኑ ታውቋል፡፡ በተቃዋሚነት የሚጠረጠሩ መምህራንና ተማሪዎች ተንቀሳቃሽ ስልኮችን እንዲጠለፉ ተደራጓል፡፡ በተጨማሪም የዕለት ተዕለት የኢንተርኔት ግንኙነታቸው እየተጠለፈ እንደሚታይ ለጉዳዩ ቅርብ ከሆኑ ወገኖች መረዳት ተችሏል፡፡

በአዲስ አበባ አሰቃቂ የነፍስ ግድያዎች እየተፈጸሙ ነው

በሦስት ሰዎች ላይ እጅግ ዘግናኝ የሆነ ግድያ መፈጸሙ ነዋሪዎችን አስደንግጧል፡፡ ግድያው የተፈጸመባቸው አካባቢዎች የሚኖሩ መንግስት የተባለ ተቀዋም የመኖሩ ጉዳይ እንደሚያጠራጥራቸው በምሬት ሲናገሩ ተሰምተዋል፡፡ ሁለት ሰዎች ታህሳስ 25 ቀን 2008 ዓ.ም. በግምት ከምሽቱ አምስት ሰዓት አካባቢ የረር ተብሎ በሚጠራው አካባቢ በስለትና በዱላ ተቀጥቅጠው ተገድለዋል፡፡ የድረሱልን ጪኸት ያሰሙ የነበሩትን የሟቾቹን ጩኸት ሰምቶ የግቢ በር ከፍቶ የወጣ አንድ የጥበቃ ሠራተኛም በስለት ተወግቶ ህይወቱ አልፏል፡፡ በማግስቱ በታህሳስ 26 ቀን 2008 ዓ.ም. ጉር ሾላ አካባቢ እንዲሁ አንድ ግለሰብ ተገድሏል፡፡ ጥቂት የማይባሉ ሰዎች ግድያዎቹን የወያኔ ድርጊት እንደሆኑ በቁጭት ያስረዳሉ፡፡ ይህ ዘገባ እስከ ተጠናከረበት ጊዜ ድረስ የሁሉም ገዳዮች አለመያዛቸው ጥርጣሬውን ያጠናክረዋል፡፡ ወያኔ ተቃዋሚዎችን እያፈነ በዚያውም በሕዝብ ላይ ሽብርን እያስፋፋ መሆኑ ለማንም ስውር አይደለም ተብሏል።

የካራቱሪ ስራ አሲካያጅ በአለም አቀፍ ደረጃ የውሳኔ ማገጃ አገኘሁ አለ

ለወያኔ ባለስልጣኖች ጠርቀም ያለ ጉቦ በመክፈል ከ100ሽ ሄክታር በላይ የጋምቤላ ለም መሬት ተሰጥቶት የነበረውና በቅርቡ ኮንትራቱ ተሰርዟል የተባለው የካራቱሪ ኩባንያ ስራ አስኪያጅ በዚህ ሳምንት ለጋዜጠኖች በሰጠው መግለጫ በዓለም አቀፍ ደረጃ የውሳኔ ማገጃ ያገኘ መሆንና ጉዳዩን በአለም አቀፍ አደራዳሪዎች አማካይነት በስምምነት እንዲወሰን የጠየቀ መሆኑን ገልጿል። በወያኔ አገዛዝ በኩባንያው ላይ የተወሰደው እርምጃ ስምምነቱን የሚጥስ እና ህጋዊ ያልሆነ ውርስና ዘረፋ ስራ መሆኑን ስራ አሲኪያጁ ጠቅሶ ጉዳዩ በዓለም አቀፍ ደረጃ እንዲያልቅ የሚታገል መሆኑን ተናግሯል። በወያኔ አገዛዝ የተዘረዘሩት ክሶች ከእውነት የራቁ ናቸው ካለ በኋላ ኩባንያው ስራውን በተገቢው መንገድ ለማካሄድ ያልቻለው ወያኔ ተግባራዊ ባደረጋቸው ማዕቀቦች ምክንያት መሆኑን ተናግሯል። የወያኔ ባለስልጣኖች የኩባንያው ምርት ወደ ውጭ እንዳይላክ በመከልከላቸው 180 ሚሊዮን ዶላር የሚሆን ኪሳራ ያደረሰበት መሆኑና እንዲሁም በደቡብ ሱዳን የጸጥታ ሁኔታ ምክንያት ከሱዳን ነዳጅ እንዳይገባ በመከልከሉ ኩባንያው የሚፈለገውን ያህል ሊሰራ አለመቻሉን ገልጿል። 100 ሺ ሂክታር መሬት በጉቦ የተሰጠው ካራቱሪ ለተወሰደብት መሬት ካሳ እንዲከፈለው ጠይቋል። ወያኔ 3.3. ሚሊዮን ሂክታር የኢትዮጵያን ለም ቦታዎች በአነስተኛ ገንዘብ ለባዕዳን ባለሃብቶች ለመቸብቸብ አዘጋጅቶ በርከት ያለውን ለባዕዳን ባለሃብቶች የሸጠ መሆኑ የሚታወስ ሲሆን እስካሁን ድረስ ለባእዳን ከተሰጡት መካከል ለአገሪቱ ውጤት ያስገኘ አለመኖሩም ተረጋግጧል።

የሳዑዲ አረቢያ መንግስት አንዲት ኢትዮጵያዊትን አንገቷን በሰይፍ በመግጣት የግድያ ቅጣት ፈጸመባት

የሳኡዲ አረቢያ መንግስት እሁድ ዕለት ያኒት ዳምጤ ፋሪድ የተባለቸውን ኢትዮጵያዊት አንገቷን በሰይፍ በመቅላት የግድያ ቅጣት የፈጸመባት መሆኑ ታውቋል። ኢትዮጵያዊቷ አሰሪዋን የሳኡዲ ተወላጅ በመጥረቢያ ገድላለች፤ ገንዘብና ወርቅ ሰርቃለች ተብላ የተከሰሰች ሲሆን ያኒት እርምጃውን መውሰዷን ማመንና አለማመኗን እንዲሁም ስለፍርዱ ሂደትና

ማረጋገጫ የተሰጠ ዝርዝር መረጃ የለም። በሳኡዲ ውስጥ የሚኖሩት ስደተኞች ከፍተኛ ኢሰብአዊ የሆነ በደል እንደሚደርስባቸው በየጊዜው የተገለጸ ሲሆን እርምጃውን ወስዳ ከሆነም ይህ ለማድረግ ያስገደዳት የደረሰባት ከፍተኛ በደል ሳይሆን አይቀርም የሚሉ ታዛቢዎች አሉ። የሳኡዲው ፈላጭ ቆራጭ አገዛዝ ባለፈው የፈረንጆቹ ዓመት ብቻ ከ155 በላይ የሆኑ ሰዎችን አንገት በመቅላት በአሰቃቂ ሁኔታ የግድያ ቅጣት በመፈጸም የአለምን ክብረ ወስን የያዘ መሆኑን የሰብአዊ መብት ተከራካሪ ድርጅቶች ዘግበዋል።

በቱርክ፤ በኢራክና በኢንዶኖዢያ በቦምብ አደጋ ሰዎች ሞቱ

በዚህ ሳምንት በቱርክ ዋና ከተማ በኢስታንቡል ቱሪስቶች በሚያዞትሩበት ቀበሌ አንድ አጥፍቶ ጠፊ ባፈነዳው ቦምብ 10 ሰዎች ህይወታቸውን ያጡ ሲሆን ሌሎች 15 ሰዎች መቁሰላችው ታውቋል። ከሞቱት መካከል ስምንቱ የጀርመን ዜጎች ሲሆኑ ከቆሰሉት መካከል ደግሞ ሁለቱ ከፍተኛ ጉዳት ደርሶባቸዋል ተብሏል። ቦምቡን ያፈነዳው አጥፍቶ ጠፊ በ1980 ዓም የተወለደ የሶሪያ ተወላጅ መሆኑን ጉዳዩን የሚመርምሩት የቱርክ የጸጥታ ኃላፊዎች የገለጹ ሲሆን አይሲስ በሚባለው አሸባሪ ቡድን የተላከ መሆኑ ተነግሯል። በዚሁ በያዝነው ሳምንት ውስጥም በኢራክ ዋና ከታማ በባግዳድ በተለያዩ ቦታዎች በአይሲስ ታጣቂዎች በተካሄዱ ተኩሶችና የቦምብ ፍንዳታዎች ባጠቃላይ 51 ሰዎች የሞቱ መሆናችውንና በርካታዎች መቁሰላችውን በመጥቀስ የዜና ምንጮች ዘግበዋል። በተመሳሳይ ዜና ዛሬ በኢንዶኔዢያ ዋና ከተማ ጃካርታ ውስጥ በተለያዩ ቦታዎች የቦምብ ፍንዳታና የተኩስ ጥቃቶች ተካሂደው ሰባት ሰዎች መገደላቸውንና ከሃያ በላይ መቁሰላችውን የኢንዶኔዢያ ባለስልጣኖች ገልጸዋል። ከተገደሉት መካከል አምስቱ ጥቃቱን ያደረሱ ግለሰቦች መሆናችው ሲታወቅ ለጥቃቱ አይሲስ የተባለው ቡድን ኃላፊነትን ወስዷል ተብሏል። ጥቃቱን ያቀነባረው ባህሩን ናይም የተባለው ግለሰብ መሆኑና ከዚህ ጋር በተያያዘ ሶስት ሰዎች መያዛቸውን የኢንዶንዥያ ፖሊሶች ገልጸዋል። ከተያዙት ሰዎች ውስጥ አንደኛው ቦምብ በመስራት የሰለጠነ ሲሆን ሁለተኛው የመሳሪያ እውቀት ያለው ሶስተኛው ደግሞ የሃይማኖት አስተማሪ መሆኑ ታውቋል። ባህሩን ናይም ከአራት ዓመት በፊት ያልተፈቀደ መሳሪያ በመያዝ ለአንድ ዓመት ታስሮ የተለቀቀ ሲሆን በአሁኑ ወቅት ከአይሲስ በሚደርሰው ገንዘብ በደብብ ምስራቅ እሲያ የአሲስ ደጋፊ የሚሆኑትን ለማሰባሰብ ጥረት እያደረገ እንደነበር ለመረዳት ተችሏል።

አልሸባብ የአፍሪካ ህብረት የሰላም አስከባሪ ኃይል የጦር ሰፈርን አጥቅቶ 60 ወታደሮች ገደልኩ አለ

በዚህ ስምንት በደቡብ ሶማሊያ ኤል አዲ በምትባለው ከተማ ውስጥ በተሰማራው የአፍሪካ ህብረት የሰላም አስከባሪ ኃይል ጦር ሰፈር ላይ የአልሸባብ ታጣቂዎች ጥቃት አድርሰው የጦር ሰፈሩን ሙሉ በሙሉ የተቆጣጠሩት መሆናችውን የቡድኑ ቃል አቀባይ ገልጿልዋል። ቃል አቀባይ በተጨማሪ በሰጠው መግለጫ በጦር ሰፍሩ የነበሩት ከ60 በላይ የሚሆኑ የኬኒያ ወታደሮችም የተገደሉ መሆናችውን አስረድቷል። የከተማዋ ነዋሪዎች ለቢብሲ የዜና ወኪል በሰጡት መረጃ የአልሸባብ ወታደሮች በከተማዋ ውስጥ ሰንደቅ ዓላማቸውን ያውለበለቡ መሆናቸውንና የሞቱ ወታደሮችን አስከሬን እያዞሩ ሲያሳዩ እንደንበር ገልጸዋል። የኬኒያ ወታደራዊ ቃል አቀባይ በመጀመሪያ ዜናውን ቢያስተባብልም ጥቃቱ የ በኬኒያ ወታደሮች ላይ መፈጸሙን የአገሪቱ ፕሬዚዳንት አምነዋል።

በቡርኪና ፋሶ በአንድ ሆቴል ውስጥ በደረሰ ጥቃት የ18 አገሮች ዜግነት ያላቸው 23 ሰዎች ሞቱ

በቡርኪና ፋሶ ዋና ከተማ በኡጋዱጉ አንድ በሚገኝ አንድ ትልቅ ሆቴል እና በአካባቢው ባለው ቡና ቤት ውስጥ በዚህ ሳምንት የታጠቁ ኃይሎ ጥቃት ሰንስዘረው በርካታ ሰዎች አግተው እንደነበር ተዘግቧል። ሰዎችን ለማስፈታት በተደረገው የተኩስ ልውውጥ የ18 የተለያዩ አገሮች ዜጎች የሆኑ 23 ሰዎች የሞቱ መሆናቸውና ከሞቱቱ ውስጥ አራቱ ታጣቂዎቹ መሆናቸው ታውቋል። በእስላማዊ ማግረብ የአልቃይዳ ክንፍ እየተባለ የሚጠራው አሸባሪ ቡድን ለጥቃቱ ኃላፊነቱን ወስዷል። በቅርቡ የተመረጡት የቡርኪና ፋሶ ፕሬዚዳንት ቅዳሜ ጠዋት በቦታው ተገኝተው በሰጡት መግለጫ 150 የሚሆኑ ታጋቾችን ከታጣቂዎች ነጻ ለማድረግ የተቻለ መሆኑን ተናግረዋል።

The post ፍካሬ ዜና:- በአፍሪካ ቀንድ እየታየ ያለው የኃይል አሰላለፍ ወያኔን እያራደው መሆኑ ታወቀ | የካራቱሪ ስራ አሲካያጅ በአለም አቀፍ ደረጃ የውሳኔ ማገጃ አገኘሁ አለ appeared first on Zehabesha Amharic.

ፍ/ቤቱ የአቃቤ ህግ የደህንነት መ/ቤት ማስረጃ ‹ኦርጅናሉ› እንዲቀርብ አዘዘ

$
0
0

በነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተር

በእነ ዘላለም ወርቃገኘሁ የክስ መዝገብ በሽብር ከተከሰሱበት በሥር ፍርድ ቤት በነጻ ተሰናብተው አቃቤ ህግ በጠየቀባቸው ይግባኝ ጉዳያቸው በጠ/ፍ/ቤት እየታየ የሚገኙት የፖለቲካ ፓርቲዎች አመራሮች ከብሄራዊ ደህንነት ተገኘ የተባለው የአቃቤ ህግ ማስረጃ ‹ኦርጅናሉ› እንዲቀርብ ትዕዛዝ ተሰጠ፡፡
በእነ ሀብታሙ አያሌው መዝገብ የተከፈተው ይግባኝ ላይ የተካተቱት አቶ ሀብታሙ አያሌው፣ አቶ አብርሃ ደስታ፣ አቶ ዳንኤል ሺበሽ፣ አቶ የሺዋስ አሰፋ እና አቶ አብርሃም ሰለሞን ዛሬ ጠ/ፍ/ቤት ቀርበው ብይን ያገኛሉ ተብሎ ሲጠበቅ ተለዋጭ ቀጥሮ ተሰጥቶባቸዋል፡፡
ፍርድ ቤቱ እንዳለው አቃቤ ህግ በስር ፍርድ ቤት አልተመረመረልኝም ያለው ከብሄራዊ ደህንነትና መረጃ ማዕከል የተገኘው ማስረጃ፣ ማስረጃ ሳይሆን የመረጃ ትንተና የተሰጠበት ስለሆነ ‹ኦርጅናሉ› መረጃ ቀርቦ እንዲመረመር ትዕዛዝ ሰጥቷል፡፡
‹‹መረጃው እንደወረደ መቅረብ አለበት፤ ከስልክም ሆነ ከፌስቡክ ወይም ከኢሜል ተገኘባቸው የተባለው ማስረጃ ቃል በቃል ይቅረብ፡፡ ትንታኔ የተሰጠበት ሳይሆን ቀጥታ ቃሉ ይቅረብልን›› ብሏል ፍርድ ቤቱ፡፡
አቶ አብርሃም ሰለሞንን በተመለከተ በስር ፍርድ ቤት የተሰማባቸው 3ኛ የአቃቤ ህግ ምስክር ሙሉ ቃልም አቃቤ ህግ ይዞ እንዲቀርብ ታዝዟል፡፡ ፍ/ቤቱ አቃቤ ህግ የታዘዘውን ማስረጃ ይዞ መቅረቡን ለመጠባበቅ ለጥር 24/2008 ዓ.ም ቀጠሮ ሰጥቷል፡

The post ፍ/ቤቱ የአቃቤ ህግ የደህንነት መ/ቤት ማስረጃ ‹ኦርጅናሉ› እንዲቀርብ አዘዘ appeared first on Zehabesha Amharic.


የአቶ ግርማ ካሳን የትብብር ሀሳብ ለማዳበር –ይገረም አለሙ

$
0
0

Unity

በቅድሚያ በሁለት ጉዳዮች ለአቶ ግርማ ያለኝን  አድናቆት  ልግለጽ፡፡  የመጀመሪያው የሀገራችንን ፖለቲካ አስመልክቶ ከርቀት ሆነው ያለምንም መታከትና  ተስፋ መቁረጥ  ለበርካታ አመታት በየማህበራዊ ድረ ገጾች ሀሳባቸውን በመግለጻቸውና  ሁለተኛ  ተስፋ ያደረጉበትና በኩራት የተናገሩለት ህብረትም ሆነ ድርጅት እንዳይሆኑ ሲሆኑ ተስፋ ባለመቁረጥ  ፓርቲዎች ህብረት ፈጥረው ለማየት ባላቸው ጉጉት በሚያደርጉት ውትወታ በእጅጉ አደንቃቸዋለሁ፡፡

 

የግዞት ዘመናችንን ካራዘሙት ምክንያቶች ሁሉ በቀዳሚነት የሚጠቀሰው የተቃውሞው ሰፈር መተባበር ባለመቻሉ መሆኑ አሌ የሚባል አይደለም፡፡ ከፖለቲከኞቹ ሕዝብ እያቀደመ፤ ታቅዶ ከሚደረገው ሁኔታዎች የሚፈጥሩት ክስተት እያየለ የሚፈጠሩ አጋጣሚዎች ውጤት አልባ ሆነው የሚያልፉት በዚሁ ፖለቲከኞች ተባብረው መታል ባለመቻላቸው  አንደሆነ እሙን ነው፡፡ ይህም በመሆኑ ነው በኦሮምያ የተቀሰቀሰው የህዝብ ተቃውሞ የመተባበርን ጥያቄ ወቅታዊና አጣዳፊ ያደረገው፡፡ መቼም መሪነታችንን አናጣለን ብለው ከሚሰጉት የድርጅት  ሊቀመንበሮች በስተቀር የድርጅቶችን ሲሆን ተዋህዶ ካልሆነም ትብብር ፈጥሮ መታገልን የሚጠላ የለም፡፡

እኔም ፓርቲዎች በየጎራቸው ተሰባስበው ቁጥራው አንሶ እንዲገኙ እነዚህ ደግሞ በሚስማሙበት ተስማተው ለማይስማሙበት መፍትሄ አስቀምጠው በኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ ስርዐት መመስረት በሚል የጋራ አጀንዳ በትብብር ሲታገሉ ማየትን የምናፍቅ በመሆኔ ነው የአቶ ግርማን የትብብር ሀሳብ ለማዳበር ጥያቄዎችን የማነሳው፡፡

 

አቶ ግርማ በወጪ ያለውን ትግል ያረዳል ያልኩትን የመፍትሄ ሀሳብ ይዤ መጥቻለሁ ባሉበት ጽሁፋቸው በማለት ከኢትዮጵያ ውጪ የሚገኙ ፓርቲዎች በዚህ መንገድ ቢተባሩ ይበጃ ያሉትን ሀሳባቸውን ገልጸዋል፡፡ የዚህች አስተያየት መነሻ ምክንያትም ይሄ ሀሳባቸው ሲሆን የአስተያየቴ ዓላማ አቶ ግርማ   በጽሁፋቸው ያነሱዋቸውን አንዳንድ  ጉዳዮች ይበልጥ ግልጽ አድርገውና አዳብረው እንዲያቀረቡዋቸው ጥያቄዎችን በማቅረብ ለማገዝና ለማበረታታት ነው፡፡

 

በሀገራችን ብዙ ትብብሮች መታሰባቸውን ሰምን የውሀ ሽታ ሆነው የሚቀሩት፣ መመስረታቸው ተነግሮን ለቁም ነገር ሲበቁ የማይታዩት ብዙ ተወርቶላቸው የእንቧይ ካብ ሆነው የሚቀሩት ዋናው ምክንያት በጠንካራ መሰረት ላይ አለመቆማቸው ነው፡፡  መተባበር የሚፈጥሩት ፖለቲከኞች ተነጋግረው ተማምነው በርዥሙ አቅደው ሳይሆን በወቅታዊ ሁኔታ ግፊት ወይንም በሌላ ወገን (ህብረተሰቡ ) አስገዳጅት  የሚያከናውኑት በመሆኑ ሳይወለድ ይጨነግፋል አለያም ተወልዶ ዳዴ ማለት ሲጀምር ይከስማል፡፡

 

በመሆኑም ሰሞነኛው የሀገራችን የፖለቲካ ትኩሳት ፖለቲከኞቹን ከእንቅልፋቸው የሚቀሰቅስና ለመተባበርም በቂ ምክንያት ቢሆንም የመተባበሩ ስራ በጠንካራ መሰረት ላይ እንዲቆም የሚያስችል ስራ በቀዳሚነትና በፍጥነት መሰራት አለበት፡፡ የትናንቱ ዛሬም እንዳይደገም በሚያስችል ጠንካራ መሰረት ላይ እንዲቆም የሚያስችሉት ተግባራት መከናወን አለባቸው፡፡ የአቶ ግርማ የትብብር ሀሳብ ግን ይህን የሚጠቁም ነገር የለውም፡፡ አቶ ግርማ የፓርቲዎች  ትብብር የሚል ነገር በሰሙ ቁጥር ድጋፋቸውን ሲሰጡ የኖሩና የደገፉዋቸው ትብብሮች ቀርቶ ተባበርን ያሉት ፓርቲዎችም ከመድረኩ ሲጠፉ  የተመለከቱ እንደመሆናቸው ችግሩን ያውቁታልና አሁን እውን እንዲሆን የምናስበው ትብብር በጠንካራ መሰረት ላይ እንዲቆም የሚያስችለው ሀሳብ ሊጠቁሙ ይገባቸው ነበር፡፡

ሌላው ቀርቶ በተለያዩ መስኮች እየተደረጉ ነው ያሉዋቸው ውይይቶች በዚህ በዚህ ጉዳይ ላይ ቢነጋገሩ በዚህ በዚህ ጉዳይ ላይ ከስምምነት ቢደርሱ ዘላቂ ትብብር ለመፍጠር ይስችላል የሚል ሀሳብ ቢለግሱ መልካም ነበር፡፡ መተባበር በስሜትና በፍላጎት ብቻ እውን የሚሆን አይደለም፡፡ እምነት ያስፈልጋል፤መተማመን ያሻል ከሁሉም በላይ ከግል ፍላጎት ጋር መፋታትን፣ የሥልጣን ጥምን አውልቆ መጣልን፣ከራስ በላይ ለሀገር ማሰብን ይጠይቃል፡፡ለዚህ ደግሞ በቅንነትና በግልጽነት መወያየት ያስፈልጋል፡፡

 

አቶ ግርማ የትብብር ሀሳብ ግዜ ወስደው አስበውበት ያረቡት ሳይሆን የወቅቱ ሁኔታ አሳስቦአቸው  ይህ ወቅት ሳያልፍ በቶሎ ተባበሩ ለማለት ያቀረቡት ነው የሚመስለው፡፡ ለዚህም ነው እንደገና በደንብ ግዜ ወስደው አስበው በድጋሚ ብቅ አንዲሉ ጥያቄዎችን የማነሳው፡፡

 

በቅጡ አላሰበቡትም ለማለት ካሰኙኝ መካከል  ትብብሩ የሚንቀሳቀሰው ሰላማዊ በሆነ መንገድ ነው። የትጥቅ ትግል የሚያደርጉ የትብብሩ አካል መሆን ይችላሉ፤ ግን የትጥቅ ትግላቸዉን ትብብሩ ከሚያደርገው እንቅስቃሴ መለየት አለባቸው። በኢትዮጵያ ዴሞክራቲክ ለዉጥ እንዲመጣ ከገዢው ፓርቲ ጋር ከመነጋገር ጀምሮ ሕዝባዊ እምቢተኝነትን እስከማድረግ የሚደርስ እንቅስቃሴ ይደረጋል። በማለት የገለጹት  በበቂ የሚያሳይ ነው፡፡በመሆኑም ከዚህ ሀሳባቸው ጥያቄ ላንሳ፡፡

አንድትብብሩ የሚንቀሳቀሰው ሰላማዊ በሆነ መንገድ ነው።  በአቶ ግርማ ሀሳብ መሰረት ትብብር የሚፈጥሩት በውጪ የሚገኙ ፓርቲዎች ናቸው፡ ታዲያ ከሀገር ውጪ ምን አይነት ሰላማዊ ትግል ነው የሚደረገው፡፡

ሁለት፤  ከሆነስ የትጥቅ ትግል የሚያካሂዱ ድርጅቶች እንዴት ነው የዚህ አካል መሆን የሚችሉት፡፡

ሶስት፤ የትጥቅ ትግል የሚያካሂዱት ትግላቸውን ትብብሩ ከሚያደርገው አንቅስቃሴ መለየት አለባቸው  ሲሉ ምን ማለት ነው፤ እንዴትስ ነው በተግባር የሚገለጸው፡፡

አራት፤ ከገዢው ፓርቲ ጋር ከመነጋገር ጀምሮ ሕዝባዊ እምቢተኝነትን እስከማድረግ የሚደርስ እንቅስቃሴ ይደረጋል ሲሉ የትኛው ነው የሚቀድመው፤ ይህ ሀሳብ አቶ ግርማ  ገዢው ፓርቲ ያለምንም አስገዳጅነት ወደ ንግግር ይመጣል የሚል እምነት ወይንም ተስፋ እንዳላቸው  ያሳያል፡፡ ባይሆን ኖሮ በተለያዩ ትግሎች በሕዝባዊ እምቢተኝነት ጭምር ገዥውን ፓርቲ በማስገደድ ይሉ ነበር፡፡

አምስት፤ወያኔ የማንነት ለውጥ አድርጎ የአቶ ግርማ ተስፋ እውን ቢሆነና መነጋገር ደረጃ ላይ ከተደረሰ  ከዛ በኋላ ህዝባዊ አምቢተኝነቱ ለምን ያስፈልጋል፡፡

ስድስት፤ ትብብሩ የሚፈጠረው ከሀገር ውጪ መሆኑን አባላቱም በውጪ ያሉ ድርጅቶች መሆናቸውን ( ስማቸውን ጭምር) ገልጸዋል፡፡ ታዲያ ከሀገር ውጪ ምን አይነት ሕዝባዊ እምቢተኝነት ነው የሚካሄደው፡፡

 

ትብብሩ አገር ቤት ለሚደረገው ትግል አጋር የሚሆን ነው። አገር ቤት ያሉትን ደርጅቶች ይረዳል፣ ይደግፋል። አገር ቤት ያሉ ሊሰሩት የማይችሉትን ይሰራል በማለት የገለጹት  በደንብ አስበውበት እንዴት ተግባራዊ መሆን እንደሚችልም አጢነውት  ከሆነ የሚከተሉትን ጥያቄዎች በመመለስ ሀሳባቸውን በጣም ግልጽና ተጨባጭ እንዲሆን ያድርጉ፡፡

 

አንድ፤ ትብብሩ በሰላማዊም በትጥቅም የሚታገሉትን በአባልነት እንደሚይዝ ነግረውናል፡፡ታዲያ አንዴት ተደርጎ ነው ሀገር ቤት ያሉ ድርጅቶች በትጥቅ የሚታገል ደርጅት አባል ከሆነበት ትብብር ርዳታና ድጋፍ የሚያገኙት፡፡ አቶ ግርማ የጸረ ሽብር ህጉን ረሱት አንዴ፡፡በሥልጣን ላይ ያለውን ኃይል በሚገባ አያውቁትም ሊያሰኝ የሚችልም ሀሳብ ነው፡፡

ሁለት፤ ቀደም ብሎ የትብብሩን ተግባር ሲገልጹ በኢትዮጵያ ዴሞክራቲክ ለዉጥ እንዲመጣ ከገዢው ፓርቲ ጋር ከመነጋገር ጀመሮ ሕዝባዊ እምቢተኝነትን እስከማድረግ የሚደርስ እንቅስቃሴ ይደረጋል ብለዋል፡፡ ከዚህ ያለፈ ትብብሩ የሚሰራው ነገር አልገለጹም፡፡ ታዲያ ሀገር ቤት ያሉ ድርጅቶች ሊሰሩ የማይችሉትን ይሰራል ሲሉ  ስራዎቹ ምን ይሆኑ፤

ሶስት፤ አንዳዴ ነገሮች ቅርብ ካለው ይልቅ በርቀት ላለው ሊታዩ ይችላሉ፡፡ እናም እኛ በሀገር ቤት ያለን ያላየናቸው ታግለው ለውጥ ለማምጣት ይችላሉ ተብሎ ተስፋ የሚጣልባቸው አይደለም ፓርቲ ሊባሉ የሚችሉ የትኞቹ ናው፡፡ አቶ ግርማ ስም ጠቅሰው ማስረጃ አጣቅሰው ሊነግሩን ቢችሉ መልካም ነው፡፡ ይህን የምለው የሌለ ነገር አለ እያልን ሀያ አራት አመት አባክነናልና ነው፡፡ አሁን ኢትዮጵያ ውስጥ በቅርብ የምናውቃቸው ፓርቲ የሚል ስም የያዙ እዛና እዚህ የጥቂት ሰዎች ስብስቦች አሉ፡፡ በተግባር ግን አንድም  ፓርቲ ለመባል የሚበቃ አይደለም ከየግል ሽኩቻና ፓርቲን የግል ንብረት ከማድረግ ወጥቶ ፓርቲ ለመሆን የሚጣጣር አንድም ስብስብ የለም፡፡

አቶ ግርማ በጽሁፋቸው  ትብብሩ 21 አባላት ያሉት ምክር ቤት ይኖረዋል  ብለው ብዙም መስመር ሳይሄዱ  የምክር ቤቱ 25 አባላት በሚከተለው መንገድ ይሰባሰባሉ፡ ይላሉ፤  ይህን የአጻጻፍ ስህተት ብለን እንለፈው ወይንስ በሁለቱ መካከል ልዩነት ኖሮ አውቀው ያሉት፣ ይሆን ግልጽ ቢያደርጉት መልካም ነው፡፡

እነዚህ 21 ም ይሁኑ 25 ድርጅቶችና ግለሰቦች በስም ዘርዝረው ሲያቀርቡ በምን መመዘኛ እንደመረጡዋቸው ግን አልገለጹም፡፡ ማሳየቱ ግን ተገቢ ይመስለኛል፡፡

ሌሎች ሊነሱ የሚገባቸው ጉዳዮች ቢኖሩም እነዚህ ይብቁኝ፣አቶ ግርማ ለእነዚህ ምላሽና ማብራሪያ ለመስጠት ጽሁፋቸውን እንደገና ሲያዩት ሌሎቹንም ተገንዝበው ምላሽ የሰጡባቸዋል የሚል ተስፋ አለኝ፡፡

የትብብር ጉዳይ በዚህ ወቅት መፍትሄ አግኝቶ  ከቃል ወደ ተግባር መሸጋገር ካልቻለ ተስፋ አስቆራጭ ይሆናልና ሁሉም በሚችለው መንገድ ግፊት ያድርግ፣ለፖለቲከኞቹ ቅርብ የሆነም ምክር ይለግስ፣ኢትዮጵያውያን ወያኔን ለመቃወም ሰልፍ ሲወጡ ፖለቲከኞቹንም ተባበሩ በማለት ይጠይቁ፡፡ ሕዝብ ለነጻነቱ እየታለ በግፍና በገፍ ሲገደል ፖለቲከኞቹ መተባበር ተስኖአቸው ማየት አሳፋሪም አሳዛኝም ነው፡፡

The post የአቶ ግርማ ካሳን የትብብር ሀሳብ ለማዳበር – ይገረም አለሙ appeared first on Zehabesha Amharic.

በሊቀጳጳስ ብጹዕ አቡነ ኤፍሬም መኖሪያ ቤት ቦምብ ፈነዳ

$
0
0

“በሊቀ ጳጳሱ እና በአስተዳደራቸው ላይ ጫና የመፍጠር ዓላማ ያለው ነው”/የሀገረ ስብከቱ ምንጮች/

ፖሊስ አምስት ተጠርጣሪዎችን ይዞ ምርመራ እያካሔደ ነው
ከደረጃቸው ዝቅ የተደረጉት የሀገረ ስብከቱ ሓላፊ ይገኙበታል
አማሳኞች፣ ጠንቋይ አስጠንቋዮችና መናፍቃን ፈተና ኾነዋል

(ሰንደቅ፤ ረቡዕ፤ ጥር ፲፩ ቀን ፳፻፰ ዓ.ም.) – በሃገር ቤት የሚታተመው ሰንደቅ ጋዜጣ እንደዘገበው
abune ephrem

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን፣ የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣ በብፁዕ አቡነ ኤፍሬም የደብረ ብርሃን መኖርያ ቤታቸው፣ ታኅሣሥ 26 ቀን 2008 ዓ.ም. ምሽት ቦምብ መፈንዳቱ ተገለጸ፡፡

በመንበረ ጵጵስናው የሊቀ ጳጳሱ መኖርያ በሚገኘው ዕቃ ቤት አጠገብ የፈነዳው ቦምቡ፣ በብፁዕ አቡነ ኤፍሬምም ኾነ በሌላ ሰው ላይ ያደረሰው ጉዳት የለም፡፡

ከፍተኛ ድምፅ የተሰማበት የፍንዳታው ስፍራ ጉድጓድ ፈጥሮ የሚታይ ሲኾን የዕቃ ቤቱ መስኮቶች ረግፈዋል፤ በመንበረ ጵጵስናው አጠገብ በሚገኘው የሀገረ ስብከቱ ጽ/ቤት ያለው የሊቀ ጳጳሱ ቢሮ መስተዋቶችም ተሰነጣጥቀዋል፡፡

የከተማው ፖሊስ ጽ/ቤት፣ አምስት የሀገረ ስብከቱን ሓላፊዎች እና ሠራተኞች ታኅሣሥ 27 እና ጥር 3 ቀን በቁጥጥር አውሎ ምርመራ እያካሔደ መኾኑ ተጠቅሷል፡፡

የሰው ኃይል አስተዳደር ክፍል ሓላፊው ቀሲስ አስቻለው ፍቅረ፣ የሕግ ክፍሉ መምህር አክሊል ዳምጠው፣ ኹለት የጥበቃ ሠራተኞች እና አንድ የሊቀ ጳጳሱ የቅርብ ዘመድ በአስተዳደሩ ፍ/ቤት በተለያዩ ጊዜያት በፖሊስ ቀርበው ከ7 እስከ 10 ቀናት ጊዜ ቀጠሮ ተጠይቆባቸዋል፡፡

ፍንዳታው በተከሠተበት ወቅት፣ ብፁዕ አቡነ ኤፍሬም የልደትን በዓል ለማክበር በመርሐ ቤቴ እንደ ነበሩ የሀገረ ስብከቱ ምንጮች ተናግረዋል፡፡

ድርጊቱ “የማስፈራራት ዓላማ ያለው ነው፤” ያሉት ምንጮቹ፥ ከክሥተቱ ኹለት ሳምንት በፊት በሊቀ ጳጳሱ የዝውውር ርምጃ የተወሰደባቸው የአስተዳደር ክፍሉ ሓላፊና ሌሎች የጥቅም ግብረ አበሮቻቸው በብፁዕ ሊቀ ጳጳሱና በአስተዳደራቸው ላይ ጫና ለመፍጠር ያቀዱበት ሳይኾን እንደማይቀር ጠቁመዋል፡፡

በአስተዳደር ጉባኤ ታይቶ በሊቀ ጳጳሱ የጸደቀ ነው በተባለው ውሳኔ÷ በሙስና፣ በባለጉዳዮች እንግልት እና በጠንቋይ አስጠንቋይነት ክፉኛ የሚተቹት የሀገረ ስብከቱ የሰው ኃይል አስተዳደር ክፍል ሓላፊ ቀሲስ አስቻለው ፍቅረ ከደረጃቸው ዝቅ ተደርገው ወደ ስታቲስቲክስ ክፍል ባለሞያነት መዘዋወራቸው ታውቋል፡፡

በሙስና፣ በመልካም አስተዳደር ዕጦት፣ አስተምህሮንና ሥርዓትን በሚፃረሩ የኑፋቄ አካሔዶች ገዳማቱን በማተራመስ እና በጠንቋይ አስጠንቋዮች ሳቢያ ከወረዳ ቤተ ክህነት፣ ከአገልጋዮች እና ከምእመናን በርካታ ምሬቶች እና አቤቱታዎች ለብፁዕነታቸው እና ለጽ/ቤታቸው ሲቀርቡ የቆዩ ሲኾን ከሰላም አኳያም አፋጣኝ መፍትሔ እንዲፈለግላቸው የዞኑ አስተዳደር ለሀገረ ስብከቱ ጽ/ቤት ማሳሰቢያ ሲሰጥ መቆየቱ ተገልጧል፡፡

በጸሎተኛነታቸው እና በአባትነታቸው ተወዳጅ የኾኑት የዕድሜ ባዕለጸጋው ብፁዕ አቡነ ኤፍሬም፣ ሀገረ ስብከቱን በሊቀ ጳጳስነት ሲመሩ ከ፳ በላይ ማስቆጠራቸውን ያስረዱት ምንጮቹ፣ የተቃጣባቸው አደጋ፣ “በግል ጥቅም ኅሊናቸው ከታወረ እና የቤተ ክርስቲያኒቱን ህልውና አሳልፎ ከመስጠት ወደ ኋላ ከማይሉ አካላት በቀር በሌላ በማንም ሊታሰብ አይችልም፤” በማለት በእጅጉ ማዘናቸውን ገልጸዋል፡፡

በሕገ ቤተ ክርስቲያኑና በቃለ ዐዋዲ ደንቡ መሠረት፣ የሀገረ ስብከት ዋና ጽ/ቤት በሀገረ ስብከቱ ለሚገኘው የቤተ ክርስቲያን አስተዳደር ከፍተኛ የሥራ አስፈጻሚ አካል ነው፡፡ በቅዱስ ሲኖዶስ የተሾመው ሊቀ ጳጳሱ፣ የሀገረ ስብከቱ ጽ/ቤት መሪና ተጠሪ ሲኾን ለአስተዳደሩም የበላይ ሓላፊ ነው፡፡ በአስተዳደር ጉባኤው የታየና የተጠና የሰው ኃይል ቅጥር፣ ዕድገት፣ የሥራ ዝውውር፣ ደመወዝ መጨመርና ሠራተኛ ማሰናበት ሊፈጸምና በሥራ ላይ ሊውል የሚችለው በሊቀ ጳጳሱ ጸድቆ መመሪያ ሲሰጥበት ነው፡፡

The post በሊቀጳጳስ ብጹዕ አቡነ ኤፍሬም መኖሪያ ቤት ቦምብ ፈነዳ appeared first on Zehabesha Amharic.

ማስተር ፕላኑን ማን አጸደቀው? ማስተር ፕላኑንስ ኦፒዲኦ የማስቆም ስልጣን አለውን? | 5 ጥያቄዎች ለኦህዴድ አባላት

$
0
0

ከ- መርጋ ደጀኔ (ኖርዌይ )

ሲጀመር የአዲስ አበባ ማስተር ፕላኑን ያጸደቀው ወያኔ ነው፡ የማስተር ፕላኑንም አፈጻጸም የሚተገብረው በወያኔ ቁልፍ ሰዎች ነው፡ ሟች ጠቅላይ ሚኒስቴር የማስተር ፕላን አሰራር እንዲሁም በአዲስ አበባ የመሬት ቅርምት ውስጥ ተጠቃሚ የሚሆኑት ማን እንደሆኑ እና ማን በአስፈጻሚነት እንደሚሰሩ ቀድመው የዘረጉት መስመር ሲሆን የሟች ጠቅላይ ሚኒስቴር ራዕይ አስፈጻሚዎች ዛሬም በማስተባበር ላይ ይገኛሉ።

ODDO 4


አዲስ አበባ ሁሌም በህብረት የሚኖሩባት ማንም ከማንም የማይለይባት ኢትዮጵያኖች በአጠቃላይ በአንድነት የሚኖሩባት የአንድነት ተምሳሌነት የነበረች ሲሆን በማህበራዊ ህይወት እንደ እድር፤ እቁብ የመሳሰሉትን በመጠቀም ህብረተሰቡ በደንብ የተዋወቀ እና የአንድነት እና የፍቅር ተምሳሌኔት የሆነች ከተማ ነበረች። ይህችን ከተማ አብረው ተዋውቀው ተሳስበው ህብረተሰቡ በሙሉ በፍቅር ይኖርባት የነበረውን ከተማ በማስተር ፕላን ሰበብ በማፍረስ የጀመሩ የህብረተሰቡን ቤትና ንብረት ብቻ ሳይሆን አንድነቱን ፍቅሩን ኢትዮጵያዊ ጽናቱን ጭምር እንደሆነ ልንገነዘብ ይገባናል።

መቼስ ከተማ መልማትንም ሆነ ማደግን የሚጠላ ህብረተሰብ አለ ለማለት ባያስደፍርም ልማቱ እና እድገቱ ለማን ነው?የሚለው ጥያቄ ሊመለስ ብቻ ሳይሆን ተመልሶ መሄድ ያለበት ጉዳይ ነው።

OPDO 2

የአዲስ አበባ ነዋሪዎች በልማት ስም ሲፈናቀሉ የተነሱትን ነዋሪዎችን እንደተላመዱት እንደተዋደዱት በአንድ ላይ ከማስፈር ይልቅ በመበታተን እንደ አዲስ ከሌላው ህብረተሰብ ጋር እንዲቀላቀሉ ማድረጋቸው የነበራቸውን አንድነት የማፍረስ ስራ እንደተሰራበት ሊታወቅ ይገባል፡ ወያኔ ሰው ሲዋደድ አንድ ሲሆን አይወድም የሰውን መዋደድና አንድ መሆን የሚጠላ ሰይጣን ብቻ ነው፡ እነዚህ ታዲያ በውስጣቸው ያነገሱት ለኛ የማይታይን ፍቅር የሚጠላ መለያየትን የሚወደውን አንግሰውት ይሆን?

ኦፒዲኦ ማስተር ፕላኑን እንደማይተገበር ብቻ ሳይሆን ሙሉ ለሙሉ መቆሙን በውሸት ቀለቧ ቴሌቭዥን ETV ላይ ብቅ ብለው ነግረውናል። ለመሆኑ ማስተር ፕላኑን ማጽደቅ ሳትችሉ በመስፋፋቱ ዙሪያ ላይ ሃሳብ ሳትሰጡ አፈጻጸም ላይ እንደ ህዝብ ሰምታችሁ ሳለ ዛሬ እንደ ሙሉ ባለስልጣን ተነስታችሁ ማስተር ፕላኑ ተሰርዟል ብላችሁ ስትናገሩ ትንሽ አይከብዳችሁም ይሄንን ቅጥፈትን ሰፊው የኢትዮጵያ ህዝብ አያውቅም ብላችሁ ይሆን ??ስለምን በህዝብ ላይ ቁማር ትጫወታላችሁ ?ጁነዲን ሳዶ ማስታወስ እንዴት አቃታችሁ ጁነዲን ሳዶን ተጠቅመው ከጨረሱ በሃላ እንደ እላቂ ዕቃ ጨርሰው ዛሬ የሚቀምሰውን መከራ ማስታወስ እንዴት አቃታችሁ፡ ጁነዲን ሳዶ የሚገረፈውን  ጸጸትን እንዴት ዞር ማየት ተሳናችሁ? ነገም እናንተ እንደ አለቀ ዕቃ  እንደምትጣሉ እንዴት ረሳችሁት?ስለዚህ ውለታም ከማያውቅ እውነትን ከሌለው የወያኔ አገልጋይ ሆናችሁ በኋላ የህሊና እዳ እንዳይኖርባችሁ ከድርጊታችሁ ትቆጠቡ ዘንድ ሳይመሽባችሁ የህዝብ አጋርነታችሁን ታሳዩ ዘንድ ጥሪ አደርጋለሁ።

OPDO1

ጥቂት ጥያቄ ለኦፒዲኦ፦

እውነት ስልጣን ካላችሁ የሚከተሉትን ጥያቄዎች እናቀርባለን፡

  1. ማስተር ፕላኑ ያጸደቀው ኦፒዲኦ ነውን?ከሆነ መቼ?እንዴት/ለምን የሚለው መልስ ይመለስ ካልሆነ ደግሞ ያላጸደቀውን ማስተር ፕላን ቆማል ለማለት ማን መብት ሰጣችሁ ?
  2. ወያኔ ጥቅም ላይና ውሳኔ ላይ ሁሌም የበላይ ሆኖ ይቀመጣል ውሳኔዎችንም ይወስናል፡ ውሳኔውንም ህዝብ ሲቃወም ጥቅሙንም ህዝብ ሲያሳጣው ባዘጋጀው መዶሻ ህዝብን መምታት ይፈልጋል ዛሬ በአዲስ አበባ ማስተር ፕላን እምቢተኝነት የተነሳው የህዝብ እምቢተኝነት ለመምታት እራሱን ኦፒዲዮ ውስጥ በመቅበር ኦፕዲኦ የተባለውን መዶሻ በማንሳት ህዝብን ለመምታት ሲነሳ እናንተም አዎ መዶሻ ነን ካላችሁ ምንም ጥቅም እንደሌላችሁ ልትቆጠሩ ስለምን እንቢ ማለት አቃታችሁ እንቢታችሁንም ተነጥቃችሃል ወይ ?
  3. እስከ ዛሬ በአዲስ አበባ ዙሪያ የተነሱት ነዋሪዎች የት ደረሱ?ምን ደረጃ ላይ ነው ያሉት? ምንስ ያህል ሰው ተነስታል በምትኩስ በቦታቸው ላይ ምን ተሰራ ?እነማን ሰፈሩ ሙሉውን መረጃ ስለምንፈልግ በተጣራ መረጃ በማቅረብ ለህዝብ ማሳወቅ ትችላላችሁ?
  4. የማስተር ፕላን ውሳኔ በማስተላለፍ ህዝብ እንቢ ሲል ብዙ ግፍና በደል ደርሶበታል ዛሬ ብቻ ሳይሆን ብዙ ዓመታት ከመጀመሪያው ጀምሮ በግፍ የተገደሉትን ኢትዮጵያዊ በትክክለኛ መረጃ ከነቁጥራቸው፡ ሟቾችንንና ተጎጅዎችን ማሳወቅ ይጠበቅባችሃል ለሞቱትም ቤተሰብ እና ለተጎዱት ህብረተሰብ ተመጣጣኝ ካሳ እንዲከፈላቸው ህጋዊ ትዕዛዝ መስጠት አለባችሁ ኦፒዲኦ ይሄንን የህዝብን መብት እና ጥያቄ መመለስ ይችላል?
  5. በማስተር ፕላኑ ዙሪያ ትዕዛዝ በመስጠት ህዝብን የገደሉና ያስገደሉ እንዲሁም በህዝብ ላይ ያልተገባ ዛቻ ያደረጉት ባለስልጣን በሙሉ ለፍርድ የማቅረብ ስራ ከተሰራ ተገቢውን ፍርድ ማሰጠት ከቻላችሁ እና የሰው ደም የጠማውን የወያኔ ጭፍጫፊ ሰራዊት ከኦሮሚያ ክልል ባአፋጣኝ ማስወጣት ይጠበቅባችኋል ይሄ ሳይሆን ግን መግለጫሁ የኢትዮጵያ ህዝብ ሊቀበላችሁ ይችላልን?።
  6. OPDO

እነዚህን እና ከዚህ ጋር ተመሳሳይነት ያላቸው በህዝብ ላይ የተፈጸመውን በደልና ግፍ መመለስ ከቻላችሁ ያኔ መግለጫዎቻችሁን ህዝቡ በአመኔታ ይቀበላል::

OPDO 5እንደዝህና የመሳሰሉት ተፈጻሚነት ሳያገኙ ግን ከኦፒዲኦ የሚሰጡትን መግለጫ የወያኔ መዶሻ ሆኖ ህዝብን እንደመምታት ነውና ይታሰብበት፡ የህዝቡን ጥያቄዎች በቀላሉ ካያችሁት ወይንም አሁን በተናገራችሁት መግለጫ ብቻ ማስተር ፕላኑ ሙሉ ለሙሉ ቆሟል በሚል የሚቋጭ መሰላችሁ ካሰባችሁ ተሳስታችሃል ትግሉ የማስተር ፕላን ብቻ ሳይሆን የፍትህ ጭምር ነው፡ ፍትህ የሚፈልግ ሰው ደግሞ ፍትህ እስካላገኘ ድረስ ከትግሉ ማንም አያቆመውም። ለዚህም ከበዳይ ጋር በዳይ ከገዳይ ጋር ገዳይ ከዘራፊ ጋር ዘራፊ ሆናችሁ በስልጣን መቀጠል የት ሊያደርሳችሁ አስባችሁ ይሆንን? ለነጻነቱ ከሚታገለው ህብረተሰብ ጎን በመሆን እራሳችሁንም ነጻ በማድረግ ህዝብ ከሚያነሳው የነጻነት ጥያቄ ጋር መቀላቀል በይፋ የምታሳውቁት መቼ ይሆን?። ሁሉም ሳይረፍድ ወደ እውነት በመምጣት የህዝብን ጥያቄ በመመለስ ዲሞክራሲያዊ ኢትዮጵያን ለመመስረት ትግል ያድርግ ህዝብ ሁሌም አሸናፊ ነው።

ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ !!!

ከ -መርጋ ደጀኔ

Email mergadejene50th@gmail.com

21-01-2016

The post ማስተር ፕላኑን ማን አጸደቀው? ማስተር ፕላኑንስ ኦፒዲኦ የማስቆም ስልጣን አለውን? | 5 ጥያቄዎች ለኦህዴድ አባላት appeared first on Zehabesha Amharic.

የስነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ኮሚሸን የንግድ ሥርዓቱ በሙስና የተዘፈቀ መሆኑን አረጋግጫለሁ አለ…(ትዕግስት ዘሪሁን)

$
0
0
ኢሕአዲግ

ኢሕአዲግ

ይህን የሰማነው ኮሚሽኑ ዛሬ የአዲስ አበባ ነጋዴዎችንና የንግድ ሥርዓት አስፈፃሚ የሆኑ የመንግሥት መሥሪያ ቤት ኃላፊዎችን ሲያወያይ ነው፡፡

ምክትል ኮሚሽነሩ አቶ ወዶ አጦ እንዳሉት የንግድ ፈቃድ ለማደስ የሚጠየቅ ጥቅማ ጥቅም አለ፣ በትላልቅ የመንግሥት ንብረትና አገልግሎት ግዢ ላይም በመቶ ሺዎች የሚቆጠር ብር ይጭበረበራል፡፡

በተጨማሪም የዕለት ተዕለት ኑሮ ጋር የተገናኘ መሠረታዊ የንግድ ሥርዓት ችግር መኖሩንም ሰምተናል፡፡

በመሠረታዊ የሸቀጣ ሸቀጥና የፍጆታ እቃዎች አቅርቦትና ስርጭት ህዝቡን እያማረረ ነው ተብሏል፡፡ የጥራት ደረጃቸውን ያልጠበቁ የንግድ ዕቃዎችም በመመሳጠር ለወጪና ገቢ ንግድ ፈቃድ እንዲሚሰጥ ደርሼበታለሁ ብሏል ኮሚሽኑ፡፡

በንግድ ስርዓቱ ላይ ያሉ የተበላሹ አሰራሮችንም አይቻለሁ፤ ብቻዬን ለውጥ ማምጣት ስለማልችል የንግዱ ማህበረሰብም ችግሩን በማጋለጥና መፍትሄ እንዲመጣ በማድረግ ሊያግዘኝ ይገባል ሲል የንግዱን ማህበረሰብ እያወያየ ነው፡፡

እንደ አለም ባንክ ግምት ከሆነ እንደ ኢትዮጵያ ባሉ ታዳጊ የአለም አገሮች 80 ቢሊየን ዶላር በየአመቱ በሙስና መልኩ ይከፈላል፡፡

 

The post የስነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ኮሚሸን የንግድ ሥርዓቱ በሙስና የተዘፈቀ መሆኑን አረጋግጫለሁ አለ…(ትዕግስት ዘሪሁን) appeared first on Zehabesha Amharic.

በዱባይ ማራቶን ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በሁለቱም ፆታ ድል ቀንቷቸዋል። ከ1-5 ባለው ደረጃ በመካከላቸውም ጣልቃ አላስገቡም

$
0
0

ዛሬ ጠዋት በዱባይ በተካሄደ የማራቶን ውድድር ላይ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በወንድም በሴቶች ከአንድ እስከ ሶስት በማሸነፍ በድል ተንበሸበሹ::

በወንዶች ተስፋዬ አበራ 2ሰዓት04ደቂቃ ከ24 ማይክሮ ሰከንድ አንደኛ በመውጣት ሲያሸንፍ ፣ለሚ ብርሃኑ 2ኛ ፀጋዬ መኮንን 3ኛ በመውጣት አሸናፊ ሲሆኑ በሴቶች ደግሞ ትርፌ ፀጋዬ 2ሰዓት ከ19ደቂቃ ከ41ማይክሮ ሰከንድ አንደኛ በመውጣት ስታሸንፍ አማኔ በሪሶ ሁለተኛ መሰለች መልካሙ ሶስተኛ በመሆን አሽንፈዋል::

በዚህም ለአትሌቶቹ እንደየ ደረጃቸው በአጠቃላይ ወደ አንድ ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር ሽልማት ያገኛሉ ተብሎ ይጠበቃል::

sport 12 sport 2

The post በዱባይ ማራቶን ኢትዮጵያውያን አትሌቶች በሁለቱም ፆታ ድል ቀንቷቸዋል። ከ1-5 ባለው ደረጃ በመካከላቸውም ጣልቃ አላስገቡም appeared first on Zehabesha Amharic.

ክርስቲያኖችን ከአክራሪዎች ጥቃት ሲታደግ መሰዋት የሆነው ሙስሊም ብሔራዊ ጀግና ተባለ 

$
0
0

ከታምሩ ገዳ

 

ሳሊህ ፋሪህ የእስልምና ሃይማኖት ተከታይ ሲሆን በሙያው ደግሞ መምህር ነበር።ታዲያ ባለፈው ታህሳስ 2015 አኤ አ የሶማሊያው ነውጠኛው እና አክራሪ ቡደን አልሽባብ ኬኒያ ውስጥ ማንዲራ ከተባለ አካባቢ ወደ ናይሮቢ ለሃይማኖታዊ በአል በሕዝብ መጓጓዣ መኪና ተሳፍረው የነበሩ ተሳፋሪዎችን በማሰቆም ክርስቲያንኖችን ከሙስሊም ተሳፋሪዎች በመለየት ሙስሊም የሆኑትን በነጻ በመልቀቅ 28ቱ ክርስቲያኖችን ወዲያውኑ ሲገደሏቸው የእሰልምና ሃይማኖት ተከታዩ ሳሊህ ከተሳፋሪዎቹ አንዱ ነበር ። ይሁን እና ሳሊህ “ክርስቲያን ወገኖቻችንን ለአክራሪዎች አሳልፈን አንሰጥም “ ከሚሉ ሙስሊም ወገኖቹ ጋር በመሰለፉ ከአክራሪው አልሸባብ ታጣቂዎች በተተኮሰበት ጥይት በእጁ እና በታፋው ላይ በደረሰበት ጉዳት ሳቢያ ናይሮቢ ከተማ ውስጥ በሕክምና ሲረዳ ቆይቶ ባለፈው ሰኞ ከዚህ አለም በሞት ተለይቷል ። 

muslim

ሰማእቱ ሳሊህ በወቅቱ ሰለነበረው መጥፎ ሁኔታ ለቢቢሲ ራዲዮ በሰጠው አማኝነት “ አሸባሪዎቹ ወደ ተሳፈርንበት መኪና መጥተው ሙሲሊሞች ካላችሁ እራሳችሁን ከክርስቲያኖች ባስቸኳይ ለዩ እናነተን አንነካችሁም ፣ በነጻ መሄድም ተችላላችሁ አሉን። እኛ ግን 62ታችን ተሳፋሪዎችን ልቀቁን አለበለዚያ ሁላችንንም እዚሁ ግደሉን አልናቸው ታጣቂዎቹ ተደናግጠው ያገኙትን ገደለው እኔንም በጥይት አቁስለውኝ ከሰፍራው ተሰውሩ ። እኔ እስከሚገባኝ ድረስ የሃይማኖት ልዩነት ካለሆነ በቀር ሁላችንም አንድ በመሆናችን ሙስሊሞች ክርስቲያኖችን ሊንከባከቡ ክርስቲያኖችም ሙስሊሞችን ከጥቃት በመታደግ በሰላም እና በጋራ መኖር የግድ ይለናል ።” ሲል ሰለ ሰላም እና መቻቻል የነበረውን ጽኑ አቋሙን ተናገሯል ።
በሙስሊም ሃይማኖት ስረአት እና ደንብ መሰረት ማንዲራ ከተማ ውስጥ ማክሰኞ እለት ስርአተ ቀብሩ የተፈጸመው ሰማእቱ ሳሊህ በኬኒያ መንግስት ዘንድ እውነተኛ ብሔራዊ ጀግና የሚል ስያሚ የተሰጠው ሲሆን የሞምባሳ አካባቢ የሙስሊሞች ካውንስል ሰብሳቤ የሆኑት ሺክ ጁማ ናጎው “ፋራህ ቅዱስ ቁራን የአንደን ሰው ህይወት ማዳን የአጠቃላይ የሰው ልጅ ዘርን ማዳን ነው የሚለውን አሰተምሮትን በተግባር የፈጸመ ትክክለኛ ሙስሊም ነው ።” ብለውታል። ሰማእቱ ሳሊህ ስላደረገው ሃይማኖታዊ እና ሰብ አዊ ተጋድሎ በክርስቲያን ወገኖቹም በኩል ታላቅ አክብሮት እና አድናቆት አልተለየውም። የኬኔያ ባብቲስት ኮንቨንሽን ቤ/ክን አስተዳዳሪ የሆኑት ዊሊንግተን ሙቲሶ “ነፍሱን ሰለክርስቲያኖች ህይወት ሲል በመያዣነት ያቀረበ ታላቅ ሰማእት ፣በሞቱ የብዙዎችን የተዛባ ሃይማኖታዊ አመለካከትን የቀየረ(ሁሉም ሙስሊሞች አክራሪነትን ይደግፋሉ ተብሎ የሚወራው ፍጹም ሃሰት መሆኑን በተግባር ያሰመሰከረ) ወገናችን ፣ ክርሰቲያኖች ዘወትር የሚኮሩበት እና የሚዘክሩት ታላቅ ሰው ነው ።”ብለውታል ።

በማንዲራ አካባቢ የሮማን ካቶሊክ ቤ/ክ ሃላፊ የሆኑት ጆን ሞሶዮካ እንዲሁ” አሸባሪዎች ሃይማኖትን ሸፋን ማድረግ እንደማይችሉ ፣ሃይማኖትም ቢሆን ከፈጣሪ ጋር መገናኛ እንጂ የሰዎች መከፋፈያ መሳሪያ ያለመሆኑን ወንድማችን ፋራህ በሚገባ አሰተምሮናል ።” በማለት ክርስቲያናዊ እና አባታዊ የሆነው ምስክረነታቸውን ሰጥተዋል። ራሺድ የተባለው የሳሊህ ወንድም በበኩሉ ለኬኒያው “ዘ ስታር “ጋዜጣ ሰለ ሟቹ ወንድሙ መሰዋትነት ሲገልጽ”የወንደሜ መሞት በኬኒያዎች መካከል የተለያዩ ሃይማኖተኞች እና የማህበረሰብ ክፍሎች እንዴት ተቻችለው እንደሚኖሩ መንገድ ጠራጊ ነው ብዩ ተሰፋ አደርጋለሁ።” ሲል ተናገሯል።
ሳሊህ ምንም እንኳን የጎረቤት ኬኒያ ተወላጅ ቢሆንም የከፈለው መሰዋትነት በየትኛውም ጠርዝ ይሁን በየትኛውም ስፍራ በጎሳ ፡በጽንፈኝነት እና በጠባብነት ለወደቁ ወገኖች ትልቅ ትምህርት አለው አርሱም ተቻችሎ እና ተፈቃቅሮ ለመኖር ዋንኛ መለኪያው የጎሳችን፣ የቋንቋችን፣ የሃይማኖታችን እና የእውቀታችን ግዝፈት እና ምጥቀት ወይም የውጫዊ አካላችን ልዩነት ሳይሆን ክቡር የሆነው ሰው መሆናችን ብቻውን ከበቂ በላይ መሆኑን ነው። ፈጣሪያችን እግዚአብሔር/አላህ የወንድማችን የሳሊህ ነፈሱን ይማረው !!!!።

The post ክርስቲያኖችን ከአክራሪዎች ጥቃት ሲታደግ መሰዋት የሆነው ሙስሊም ብሔራዊ ጀግና ተባለ  appeared first on Zehabesha Amharic.

ውሸት ሲገነፍል! –የኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች ሰላማዊ ንቅናቄ ደጋፊዎች ሕብረት

$
0
0

Muslims ከመሰረታዊ የእምነት ተግባርና ምንጭ ከስግደትና ቁርዓን ጀምሮ መስጊድ መገንባትና መንፈሳዊ ሥራዎችን ማከናወን ወንጀል ነው በሚል የወያኔ መንግስት በሙስሊሞችና እስልምና ላይ የክተት አዋጅ ነጋሪት እያስጐሰመ ነው። “የማንቂያ ደወል” በሚል ስያሜ በቅጥፈት የታጀለው ደኩሜንታሪ 1ኛ-በሙስሊሙና በክርስቲያኑ መካከል ለ14 መቶ ክፍለ ዘመን የቆየውን መተማመንና አብሮነትን ለመናድ፣ 2ኛ- በራሱ በሙስሊሙ ሕብረተሰብ መካከል ቅራኔ ለመፍጠር 3ኛ- አብዛሃኛው የኦሮሞው ሕብትረተሰብ የእስልምና ሃይማኖት ተከታይ ስለሆነ፣ ይህ ጀግና ሕዝብ በአሁኑ ጊዜ በሚያካሂደው ሕዝባዊ አመፅ ላይ በጓዳ በር በመግባት ጥቃት ለመክፈት የተደረገ ከጅምሩ የተኮላሸ ሙከራ መሆኑ ለማንም ግልጽ ነው። ከሁሉም በላይ ግን ደኩሜንታሪው የሚያንፀባርቀው ዘረኛው የወያኔ ሥርዓት የጣረሞት ፍርግጫ ላይ መሆኑንና አንድ ሓሙስ የቀረው መሆኑን ነው። —-[ሙሉውን ለማንበብ እዚህ ይጫኑ]—-

The post ውሸት ሲገነፍል! – የኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች ሰላማዊ ንቅናቄ ደጋፊዎች ሕብረት appeared first on Zehabesha Amharic.


ይድረስ ለጎንደር ሕዝብ ቁጥር #7 –“ወያኔን ማመን፤ ውሃን እንደመጨበጥ ነው”

$
0
0

Fasil , Gonder
የጎንደር ሕብረት ዛሬም እንደ አለፉት መግለጫዎቻችን፤ በጎንደር ህዝብ ላይ የሚፈጽመውን የግፍ ተግባሮች አደባባይ በማውጣት፤ አገር አድን ብሔራዊ ትግላችንን የምናጠናክርበትን ስልት የማጠናከሩን ዓላማ ግብ ለማድረስ ነው። ይህ ሲባል ግን፤ በጦርነት ተወልዶ፤ በጦርነት እያረጀ ያለው፤ አገር አጥፊው የወያኔ ቡድን፤ በወረቀት ብቻ ይወድቃል ብለን ማመናችን አይደለም። መግለጫ፤ ጠላትን ያጋልጣል። ባንፃሩም ወገንን ያሥተባብራል፤ ያደራጃል፤ ያሥታጥቃል፤ በመጨረሻም ጠላቱን ይደመሥሳል።

Read Full in PDF

The post ይድረስ ለጎንደር ሕዝብ ቁጥር #7 – “ወያኔን ማመን፤ ውሃን እንደመጨበጥ ነው” appeared first on Zehabesha Amharic.

የዕለቱ ምርጥ ካርቱን: አና ጎሜዝ (ሃና ጎበዜ) እና ሃይለማርያም ደሳለኝ

Sport: ጀግኖች አትሌቶች በዱባይ ማራቶን 2016 ድንቅ ድል ተጎናጸፉ

$
0
0

ethiopians

ነቢዩ ሲራክ
ጥር 13 ቀን 2008 ዓም

======================================
* እንኳንም ደስ ያለን !
* ከወንዶች ተስፋየ ከሴቶች ትርፊን የቀደመ አልነበረም !

1000 የሚገመቱ ተሳታፊዎች በሚሳተፉበት ዘንድሮ በዱባይ እየተካሔደ ባለው የዱባይ ማራቶን 2016 ኢትዮጵያውያን አትሌቶች የአረንጓዴውን ጎርፍ ድል በበርሃዋ የአረብ ኢምሬት ከተማ በዱባይ ደግመውታል ! አንጸባራቂውን ድል የደገሙት አትሌቶቻችን በወንድና በሴት በተደረገው ውድድር ተከታትለው በመግባት ያገኙት ውጤት በውድድሩ የበላይነትን አቀናጅቷቸዋል ።

በወንዶች አሸናፊ የሆነው ተስፋየ አበራ ዲባባ የገባበት ሰዓት 02:04:24 መሆኑ ታውቋል ። በሁለተኛነት ተስፋየን ተከትሎ የገባው የአምናው አሸናፊ ለሚ ብርሃኑ ኃይሌ 02:04:33 ሰዓት ሲያስመዘግብ በሶስተኛነት ጸጋየ መኮንን አሰፋ 2:04:46; ሰዓት ማስመዝገቡ ታውቋል ።

በሴቶች ውድድር አሸናፊ የሆነችው ትርፊ ጸጋየ ብየነ 02:18:41 ሰዓት ስታስመዘግብ አማኔ ብሪሶ ሻንኩሌ በ 02:20:48 ሰዓት በሁለተኛነት ገብታለች ። መሰለች መልካሙ ኃይለየሱስ በ02: 22:29 ሰዓት በሶስተኛነት ተከትላ መግበቷም ታውቋል !

በወንድም በሴትም በተደረገው ውድድር ከ1 እስከ 5 ተከታትለው የገቡበትን ሙሉው ውጤት እንደሚከተተለው ነው !

በወንዶች Men (All from Ethiopia)

1) Tesfaye Abera Dibaba – 2 hours: 04 minutes: 24 seconds;
2) Lemi Berhanu Hayle 2:04:33;
3) Tsegaye Mekonnen Asefa 2:04:46;
4) Sisay Lemma Kasaye 2:05:16;
5) Mula Wasihun Lakew 2:05:44.

በሴቶች Women (all from Ethiopia):

1) Tirfi Tsegaye Beyene 2:19:41;
2) Amane Beriso Shankule 2:20:48;
3) Meselech Malkamu Haileyesus 2:22:29;
4) Sutume Asefa Kebede 2:24:00;
5) Mulu Seboka Seyfu 2:24:24.

አስገራሚውን ድል በቦታው በመገኘት የታዘቡት በዱባይ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ለአትሌቶች ከፍ ታለ ሞራል ሲሰጡ መዋላቸው የአረብ መገናኛ ብዙሃምንን አትኩሮት በአድናቆት ስበውት ተስተውሏል !

እንኳን ደስ አለን !

The post Sport: ጀግኖች አትሌቶች በዱባይ ማራቶን 2016 ድንቅ ድል ተጎናጸፉ appeared first on Zehabesha Amharic.

ባለ መሰንቆውና ባለ ወለሎው (በ.ሥ)

$
0
0

“ ሮድ ደሴት” በተባለ አገር ውስጥ እንደ እንደምኖር የነገርኩት ጓደኛየ“ እና ባሣ አጥማጅነት ነው የምትተዳደረው?”ብሎኛል፡፡ ሮድ ደሴት አበሻ እጥረት ክፉኛ ከሚያጠቃቸው ክልሎች አንዱ ነው ፡፡ አሁን ምድሩም ሰማዩም ሰውም ነጭ ነው፡፡
ያገር ሰው በጣም ይናፍቀኛል፡፡ የሆነ ያበሻ ዓይነ ውሃ ያለው አልፎ ሒያጅ መንገድ ላይ ካየሁ ከሚበር አውቶብስ ላይ እንደ ጅምስ ቦንድ ተወርውሬ ወርጀ ስልኩን በቃሌ እቀበለዋለሁ፡፡ ከሁለት ሱዳናውያን ጋር የተዋወቅሁት በዚህ አጋጣሚ ነው፡፡
ያበሻ ናፍቆቴንአናቴ ላይ ሲወጣ ወደአበሻ- ጠገብ ክልሎች እቀላውጣለሁ ፡፡ ባቡሬን ጭኘ መጭ ወደ ውሻንግቶን ዲሲ! ዲሲ የውሃና የመብራት እጥረት የሌለበት አዲስአበባ ማለት ነው፡፡
ባለፈው ሳምንት ሚኒሶታ ወረድሁ፡፡ ከተማይቱ በበረዶ ተዝረክርካ የሰነፍ ቡሃቃ መስላለች፡፡ የተፈጥሮን ጨካኝነት፤ የቶማስ አልቫ ኤዲሰንን ያለም ቤዛነት ለማረጋገጥ የሚፈልግ ሚኒሶታ ይሂድ፡፡ ወይ አዲስ አበባአዱ ገነት፡፡ እብድ የያዘሽ ውበት፡፡ ሰው እንዴት ጥሎሽ ይመጣል? ሰው እንዴት ከገነት ያመልጣል?
ከመኪና ማቆምያው ተሥቼ አዳራሹ ድረስ እስክገባ ድረስ የተቀበልኩት መከራ ራሱን የቻለ ሰማእትነት ሆኖ ለትውልድ ይዘከርልኝ ፡፡ ብዙ ብርድ አጋጥሞኛል እንዲህ አራት ጃኬትና ሁለት ሱሪ ገልቦ፤ አስገድዶ የሚሠር ብርድ ደርሶብኝ አያውቅም፡፡ እድል ፈንታየ ብሎ ብሎ ደም እንደ ብይ በሚጠጥርበት፤ ያፍንጫ ጸጉር እንደጃርት ወስፌ በሚቆምበት አገር ይጣለኝ፡፡ ደሞ እቺም ኑሮ ሆና “በርገርህን እየገመጥክ ትደነፋለህ አይደል?” የሚል ብሽቅ መልክት ይልኩልኛል።ባለመልክቱ! እስቲ ያዲሳባን የጧት ጸሐይ፤ በበርገር ለውጠኝ!!

 

bewektu
ሳይደግስ አይጣላም በህይወቴ ባካል ላገኛቸው ከምፈልጋቸው ሰዎችአንዱ የሆነውን ጋዜጠኛ ሰሎሞን ደሬሳን አገኘሁት፡፡ ሰሎሞን ፈላስፋ ነው፡፡የመጀመርያው የሥእል ሓያሲም ነው፡፡ በኦሮምኛ ፤አማርኛ እንግሊዝኛና ፈረንሳይኛ የሚራቀቅ ሊቅ ነው፡፡ ወዳጅ ባታደርገው እንኳ ለፍልምያ የምትመርጠው ሰው ነው፡፡ እንድታስብ የሚገፋፋህ ፤አርፈህ እንድትቀመጥ የማያደርግህ ሰው ማግኘት መታደል አይደል? መጣጥፎቹ ተሰብስበው በመጽሐፍ አለመውጣታቸው ያስቆጫል፡፡ ”ልጅነት ” የምትል በዘልማዳዊው የአማርኛ ስነግጥም ላይ የሸፈተች የግጥም መደብል ሲያሳትም እንደ መናፍቅ ተቆጥሯል፡፡ የትውፊት አስጠባቂው አቤ ጉበኛ በሰሎሞንን ግጥምና በዳኛቸው ወርቁ ልቦለድ ላይ ለማላገጥ “ጎብላንድ አጭበርባሪው ጦጣ”የሚል መጽሐፍ እስከማሳተም ሂዷል፡፡ የአቤ ጎብላንድ ዛሬ በታሪክ ቅርጫት ውስጥ ተጥላለች፡፡ የሰሎሞንና የዳኛቸው መጽሐፎች ግን ገቢያ ላይ በጣም ይፈለጋሉ፡፡ ለምሳሌ ስለባህል ግብዝነት በተነሣ ቁጥር ይችን የሰውየውን ግጥም ማን ይረሣታል?
በኢትዮጵያ ባልጎ መታየቱ
ሳይሆን ቂንጥር ማስቆረጡ
ህጻኗን ልጅ እንደ ቆዳ መስፋቱ
መባለጉ
ኣፉን ሞልቶ” ቂንጥር “ ብሎ መጥራቱ
የሆነ ጊዜ ላይ ስብሐት ገብረእግዚኣብሄር ስለወዳጁ ስለሰሎሞን ”ከሸክስፒርና ከዳንቴ ቀጥሎ ትልቁ ባለቅኔ ሰሎሞን ነው” ብሎ ጻፈ፡፡ ላዲስ ነገር ጋዜጣ የሚሆን ቃለመጠይቅ ሳደርግለት“ሰሎሞንን በዓለም ሦስተኛ ገጣሚ አድርገህ ጽፈሐል፤ አግባብ ነው?”አልኩት፡፡
“እንደዛ ብያለሁ?”
“ኣዎ”
ስብሐት ትንሽ አሰበና መለሰ፤ “ እንዲህ ያልኩት በጣም በናፈቀኝ ሠአት መሆን አለበት“
ከሥነጽሁፉ ምሽት በበኋላ የኢትዮጵያ ተማሪዎች ማኅበር ”ሬድ ሲ” ሬስቶራንት ራት ጋበዙን፡፡ እንደምንም እየተንፏቀቅሁ ከሰሎሞን አጠገብ ያለውን ቦታ ያዝኩ፡፡ ይችን ብርቅ አጋጣሚ ተጠቅሜ ከልጅነት እስከ ሽበት ያሳለፈውን ገድሉን አናዝዘዋለሁ ብየ አሰብኩ፡፡አልቀናኝም፡፡ ከሰለሞን ጋር ጨዋታ እንደ ጀመርሁ ከኋላየ ባለጌ ወንበር ላይ የተቀመጠ ተስተናጋጅ፤ ባንገት ጥምጥሜ ጎትቶ ካዞረኝ በኋላ” ቢራውን ትተህ ለምን ጠንከር ያለ ነገር አትወስድም?”በሚል ጥያቄ ጠመደኝ፡፡ ቢራውን ትቸ ጠንከር ያለ ነገር የማልወስድበትን ሰባት ምክንያት ስዘረዝር ራቱ ተገባድዶ ከፍ አለ፡፡
ከእራት በኋላ አዝማሪው ወደ መድረክ ወጣና ማሲንቆውን ማስተከዝ ጀመረ ፡፡ በቤቱ ያለው ሰው በማሲንቆ ዜማ ታጅቦ ወደ ግል ወሬው ተጠመደ፡፡ “ኣንድ ኮርኔስ እዚህ ጋ ያዘዘ ማን ነው?” የሚለው ያስተናጋጇ ድምጽ ካዝማሪው እንጉርጉሮ በላይ ጠብድሎ ይሰማኛል፡፡ ሰሎሞን ከወንበሩ ተነሥቶ በዝግታ እየተራመደ ወደ መድረኩ ከወጣ በኋላ አዝማሪውን ሸልሞ አጠገቡ ቁጭ አለ፡፡ ዓይኑን ለበስ አድርጎ እልምም !! በማሲንቆው ተሳፍሮ የት ደርሶ ይሆን? ወለጋ-አዲስአበባ – ደጃች ውቤ ሠፈር- ፤ የከተማ መኮንን ክራር – ምኒልክና ጊዮርጊስ በፈረቃ ከሚጋልቡት የአራዳ ፈረስ፡፡
ልጅነት በተባለቸው መድብሉ ስለአንድ የውቤ በረሃ ጀግና በጻፈው መወድስ ውስጥ እኒህ መስመሮች ተካትተዋል፡፡
”ደኑ ርቆት፤
መንገዱ ጠፍቶት
ጓዱ ረስቶት
በጨለማ ቤቱን ስቶት“
ዛሬ እኒህ መስመሮች በግዞትና በስደት ሰጥመው የቀሩ ድንቅ ኢትዮጵያውያንን ሁኔታ የሚገልጹ አድርጌ ብተረጉማቸው ማን ይፈርድብኛል?
( ወዳጄ ገጣሚ ዮናስ አንገሶም ኪዳኔ የሰሎሞንን መጽሐፎች ስለሰደድክልኝ ምስጋናየ ይድረስህ፡፡)

The post ባለ መሰንቆውና ባለ ወለሎው (በ.ሥ) appeared first on Zehabesha Amharic.

አርቲስት ሚኪያስ መሐመድ ኢትዮጵያ ገባ |አዳዲስ ክሶች እየመጡበት ነው ተባለ

$
0
0

Mikiyas

(ዘ-ሐበሻ) ከ6 ነጋዴዎች የጎማ ንግድ አስነግዳችኋለሁ በሚል ገንዘባቸውን ከወሰደ በኋላ ተሰውሯል ተብሎ ክስ የቀረበበት አርቲስት ሚኪያስ መሐመድ ዘ-ሐበሻ ከዚህ ቀደም በዘገበችው መሠረት በሽምግልና ወደ ሃገር ቤት መመለሱ ተሰማ::

የዘ-ሐበሻ ምንጮች እንደገለጹት አርቲስቱ ዛሬ አዲስ አበባ የገባ ሲሆን ምናልባትም በሰይፉ ፋንታሁን የራድዮ ወይም የቲቭ ፕሮግራም ላይ ቀርቦ ስለቀረበበት የማጭበርበር ክስ ሊያስረዳ ይችላል:: በአርቲስቱ ገንዘብ ከተወሰደባቸው ሰዎች መካከል አንዱ የሆነው ድምፃዊ ታደለ ሮባና ዮኒ ቬጋስ ከአዲስ አበባ ወደ አሜሪካ በሽምግልና የተላኩ መሆኑን ዘ-ሐበሻ ባለፈው ሳምት መዘገቧ ይታወሳል:: አርቲስቱ ወደ ኢትዮጵያ ለመመለስ መስማማቱንም ዘሐበሻ ዘግባ ነበር::

ዛሬ ከአዲስ አበባ የደረሰን መረጃ እንደሚያመለክተው ከሆነ አርቲስቱ ወሰዳቸው ከተባላቸው የ6 ነጋዴዎች የሚሊዮኖች ብር በተጨማሪ ሌላ የ300 ሺህ ብር ክስ ተመስርቶበታል:: ሊታሰር ይችላል የሚሉ መረጃዎችም አሉ::

The post አርቲስት ሚኪያስ መሐመድ ኢትዮጵያ ገባ | አዳዲስ ክሶች እየመጡበት ነው ተባለ appeared first on Zehabesha Amharic.

Viewing all 15006 articles
Browse latest View live