Quantcast
Channel: Ethiopian News | ዘ-ሐበሻ | Latest News Provider | News For All
Viewing all 15006 articles
Browse latest View live

‹‹በእውነተኛው ዓለም እየኖርኩት ያለውን ህይወት ነው ድራማው ላይ እየሰራሁ ያለሁት›› ተዋናይትና ሲቪል ኢንጂነር አዚዛ አህመድ

$
0
0

 

ከፊልም ሥራ ጋር የተዋወቀችው ከ10 ዓመታት በፊት ቢሆንም በሙሉ ኃይሏና ጊዜዋ በኢንዱስትሪው ውስጥ ተጠቃሽ ባለሙያ የሆነችው ግን ከጥቂት ዓመታት በፊት ነው፡፡ 8 ለእይታ የቀረቡ ፊልሞች ላይ የተወነች ሲሆን ሁለቱ ደግሞ በቅርቡ ይወጡላታል፡፡ የአዱኒስ ድርሰት በሆነው በ‹‹መለከት›› ድራማ ዋና ገፀባህርይን ተላብሳ በመጫወቷም እናውቃታለን፡፡ የዛሬዋ እንግዳ ተዋናይት እና ሲቪል ኢንጂነር አዚዛ አህመድ፡፡

aziza ahmed meleket

ጥያቄ፡- ስምሽና ሥራሽ ፊልምንና ድራማ ለሚከታተሉ አንባብያን አዲስ ባይሆንም አዚዛ አህመድ የትነው የተወለደችው?

አዚዛ፡- ጅማ ነው የተወለድኩት፡፡ እትብቴም የተቀበረው እዛው ነው፡፡ የልጅነቴን ጊዜ ጨምሮ የኖርኩት ደግሞ አዲስ አበባ ነው፡፡ ተመልሶ የመሄድ ዕድሉም ስላልነበረኝ ስለ ጅማ ብዙ የማስታውሰው ነገር የለኝም፡፡ በቅርብ እንደምሄድ ተስፋ አደርጋሁ፡፡

ጥያቄ፡- ፊልሙና ድራማው የሙሉ ቀን ስራሽ ነው?

አዚዛ፡- አሁን የሙሉ ቀን ሥራዬ ሆኗል፡፡ በፊት ግን ትምህርት ላይ ስለነበርኩ ወጣ ገባ እያልኩ ነበር የአርት ሥራዎችን እሰራ የነበረው፡፡

ጥያቄ፡- ምንድን ነበር የምትማሪው?

አዚዛ፡- አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የሲቪል ኢንጂነሪንግ ተማሪ ነበርኩ፡፡ እሱን ስጨርስ ነው ሙሉ ለሙሉ ወደ አርቱ ፊቴን ያዞርኩት፡፡

ጥያቄ፡- ከሲቪል ምህንድስና ወደ ጥበብ ሽግግሩ አይከብድም?

አዚዛ፡- ደስ የሚል ሽግግር ነው፡፡ /ሳቅ…/ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የመጀመሪያ ዓመት ተማሪ ሳለሁ ነው 1996 ላይ ጥበብ ጠራችኝ ብዬ በቴዎድሮስ ተሾመ፣ የተሰራውንና የቀዝቃዛ ወላፈን ቁጥር ሁለት ፊልም በነበረው ፍቅር ሲፈርድ ላይ የሰራሁት፡፡ ከጨረስኩ በኋላ አምስቱን ዓመት ትምህርቴ ላይ ትኩረቴን አድርጌ ከፊልሙ ኢንዱስትሪ ርቄ ቆይቻለሁ፡፡

ትምህርቱ ከባድ ነው፡፡ በዚህ በኩል ፊልሙም ጊዜ ይፈልጋል፡፡ ስለዚህ ውሳኔ ላይ መድረስ ነበረብኝ፡፡ ስጨርስ ግን ሙሉ ለሙሉ ወደ ጥበቡ ነው የገባሁት፡፡

aziza ahmed

ጥያቄ፡- ከነዛ ዓመታት በኋላ ስትመለሺ ዘርፉ በነበረበት ነው የጠበቀሽ? አልከበደሽም?

አዚዛ፡- በጣም አድጎ ነበር፡፡ በአጋጣሚ ፍቅርና ገንዘብ የተሰኘውን ፊልም ከሚሰሩ ልጆች ጋር ተገናኘሁ፡፡ የሶስት ሴቶችን ታሪክ ሲሰሩ አንዷን ካራክተር እኔ ወክዬ እንድጫወት ነበር የመረጡት፡፡ እኔም ታሪኩን ወድጄው ስለነበር በደስታ ግብዣውን ተቀብዬ በድጋሚ ወደ ፊልሙ ስራ ገባሁ ማለት ነው፡፡

ጥያቄ፡- ጎበዝ ተማሪ ነበርሽ?

አዚዛ፡- ምንም አልልም፡፡ ውጤቴም ለክፉ ሳይሰጥ ተመርቄያለሁ፡፡

ጥያቄ፡- አስተዳደግሽ አሁን ላለሽበት ቦታ አብቅቶኛል ትያለሽ?

አዚዛ፡- በጭራሽ እንዲሁ ዝም ብሎ ሚኒ ሚዲያዎች ላይ መካፈል፣ ፕሮግራሞች በትምህርት ቤቶች ውስጥ ሲኖሩ ድራማዎችን መስራት ዕድሉ ነበረኝ፡፡ ከዛ በተረፈ ግን ቤተሰቤ ውስጥ ወደዚህ ሙያ እንድገባ የሚገፋፋኝ ሰው አልነበረም፡፡ ይበልጥ በትምህርቴ እንድገፋ ነበር ፍላጎታቸው፡፡

ጥያቄ፡- የፊልሙና የድራማው ዘርፍ አዳዲስ ተዋንያንን በደንብ ይጋብዛል?

አዚዛ፡- ኢንዱስትሪው በደንብ እየሰፋ ስለመጣ ዕድሉን የማግኘት ሁኔታው በዛው መጠን ትልቅ ነው፡፡ ደግሞም ብዙ አዳዲስ ፊቶችን በየጊዜው እያየን ነን እኮ፡፡

ጥያቄ፡- ሴት ተዋንያን ውበታቸውን በመጠቀም ፊልሞችን ይሰራሉ፡፡ እነዚህ ሰዎች ፊልሙን ፕሮዲውስ በማድረግ ወይም በሌላ መንገድ ተፅዕኖ በመፍጠር ነው ወደዚህ ስራ የሚመጡት ይሄ የኢንዱስትሪውን ዕድገት አይጎዳም?

አዚዛ፡- በቅድሚያ ፊልም ውበት ላይ ተመርኩዞ መሰራት አለበት የሚል እምነት የለኝም፡፡ እርግጥ ነው ጥሩና ሳቢ የሚባለው መልክ ቢኖርህና ፊልሙ ላይ በጥሩ ሁኔታ ብትተውን አይከፋም፡፡ ነገር ግን ያ መሰረታዊ ሊሆን አይገባም፡፡ የውጭ ሀገር ፊልሞችን ብትመለከት ፊልሙ የሚያጠነጥንባቸው ገፀ ባህሪያት የሚመረጡት፣ በዚህ መስፈርት ሳይሆን ስክሪፕቱ የሚፈልገው አይነት ሰው ሲሆኑ ነው፡፡ ያም ቢሆን የተሰጣቸውን ኃላፊነት በሚገባ እስከተወጡ ድረስ መልከኞቹንም ፊልሞቹ ላይ ብንመለከት ክፋት የለውም፡፡

 

ጥያቄ፡- በቅርቡ የወጣውን ሰኔ 30 የተሰኘውን ፊልም የማየት ዕድሉ ነበረኝ ጥሩ ሥራ እንደሆነ እኔ አምናለሁ፡፡ ፊልሙ ላይ የመሥራት ዕድል እንዴት አገኘሽ?

አዚዛ፡- ስለወደድከው ደስ ብሎኛል፡፡ ፊልሙ ላይ እንድሰራ ዕድሉን ያገኘሁት ዋጄ በሚባልና እስክሪፕቱን በፃፈው ሰው አማካኝነት፣ እንዳነብና አስተያየት እንድሰጥ በተጠየኩ ጊዜ ነው፡፡ ሥራውን እንደወደድኩት ስገልፅለት ከፕሮዲውሰሮቹና ዳይሬክተሩ ጋር ተገናኘሁ፡፡ እነሱም ከእኔ ጋር ለመስራት ፍላጎቱ ስለነበራቸው ወደ ቀረፃ ገባን፡፡

ጥያቄ፡- ሴት ተዋንያን ውበታቸውን በመጠቀም ፊልሞችን ይሰራሉ፡፡ እነዚህ ሰዎች ፊልሙን ፕሮዲውስ በማድረግ ወይም በሌላ መንገድ ተፅዕኖ በመፍጠር ነው ወደዚህ ሥራ የሚመጡት ይሄ የኢንዱስትሪውን ዕድገት አይጎዳም?

አዚዛ፡- በቅድሚያ ፊልም ውበት ላይ ተመርኩዞ መሰራት አለበት የሚል እምነት የለኝም፡፡ እርግጥ ነው ጥሩና ሳቢ የሚባለው መልክ ቢኖርህና ፊልሙ ላይ በጥሩ ሁኔታ ብትተውን አይከፋም፡፡ ነገር ግን ያ መሰረታዊ ሊሆን አይገባም፡፡ የውጭ ሀገር ፊልሞችን ብትመለከት ፊልሙ የሚያጠነጥንባቸው ገፀ ባህሪያት የሚመረጡት፣ በዚህ መስፈርት ሳይሆን ስክሪፕቱ የሚፈልገው አይነት ሰው ሲሆኑ ነው፡፡ ያም ቢሆን የተሰጣቸውን ኃላፊነት በሚገባ እስከተወጡ ድረስ መልከኞቹንም ፊልሞቹ ላይ ብንመለከት ክፋት የለውም፡፡

ጥያቄ፡- ከአርቲስት ሽመልስ አበራ (ጆሮ) እና ሰለሞን ሙሄ ጋር ነው ፊልሙ ላይ የተወንሽው፣ ከአንጋፋና ወጣት ተዋናዮች ጋር መስራት ምን አስገኝቶልሻል?

አዚዛ፡- በጣም ነው ደስ የሚለው፡፡ እንደ ዕድል ሆኖ ከአንጋፋ ተዋናዮ ጋር የመስራት ዕድል በተደጋጋሚ ጊዜ አግኝቻለሁ፡፡ ከእነሱ ጋር ስትሰራ ለወደፊት ስራህ ስንቅ የሚሆንልህ ልምድ ታገኛለህ፡፡ ምክንያቱም ቀደም ሲል እሱ የነበሩበትና ዛሬ እኛ ያለንበት ዓለም የተለያየ ነው፡፡ ካገኘሁት ጥሩ ልምድ ባሻገር የእውነት ሁለቱም ጥሩ ሰዎች ናቸው፣ ጥሩ ጊዜ ነው ያሳለፍኩት፡፡

aziza amhed zehabesha

ጥያቄ፡- ስንት ተከፈለሽ?

አዚዛ፡- ስነ ስርዓት! (ረዥም ሳቅ) አዚዛ ውድ ነች በማስባል ስራ ልታሳጣኝ ነው?

ጥያቄ፡- በመጀመሪያ የፊልም ስራሽ ስንት አገኘሽበት?

አዚዛ፡- መጀመሪያ 5 ሺ ብር ነበር ከፍቅር ሲፈርድ ፊልም የተከፈለኝ፡፡ ከዛ ቀደም ማስታወቂያ ላይ ወይም በሌላ አጋጣሚ ስክሪን ላይ የመታየት ዕድል አልነበረኝም፡፡ ስለዚህ ጥሩ ፍራንክ ነበር ለእኔ፡፡ ቴዎድሮስም ይህቺ ልጅ ታድጋለች ብሎ ነበር፤ ያን ማድረጉ ለዛም አመሰግናለሁ፡፡

ጥያቄ፡- ምን አደረግሽት ብሩን?

አዚዛ፡- ብዙ ነገር ላይ አውያለሁ፡፡ እንደዛስ ሆኖ መቼ በቀላሉ አለቀና? ብትኖር አበድርህ ነበር፡፡ ምን አለፋህ በወቅቱ የተማሪ ሃብታም ሆኜ ነበር፡፡

ጥያቄ፡- ትልቁ ክፍያሽስ?

አዚዛ፡- በቅርቡ ለሚወጣው ፊልም ጥሩ ብር ተከፍሎኛል፡፡

ጥያቄ፡- እስካሁን ስንት ፊልሞች ላይ ተሳትፍሽ? ፊልሞቹ እነማን ናቸው? ይበልጥ የደከምሽበትና የምትወጂውንም ንገሪኝ?

አዚዛ፡- 8 ፊልሞች ላይ እስካሁን ሰርቻለሁ፡፡ ‹‹እንዳባባሉ ሁሉም ልጆቼ ናቸው›› ማለት ሳይሆን፣ በሁሉም ፊልሞች ውስጥ የተወንኳቸው ገፀ ባህሪያት የተለያዩ ናቸው፡፡ ስለዚህ ለእኔ ሁሉንም ማወዳደሩ ከባድ ነው፡፡ እስካሁን የተወንኩባቸው ፊልሞች ፍቅር ሲፈርድ፣ ፍቅርና ገንዘብ 1 እና 2፣ እኔ ፕሮዲውስ ያደረኩት ጢባጢቤ፣ ሰኔ 30፣ የጥቁር ፈርጥ፣ ሳላ ይሰኛሉ፡፡ አሁን ደግሞ ሁለት ፊልሞችን እየሰራሁ እገኛለሁ፡፡

 

ጥያቄ፡- የፊልሞችን ጥራት ለመጠበቅ አንድ ተዋናይ በዓመት ምን ያህል ፊልሞች ላይ መተወን ይኖርበታል ትያለሽ?

አዚዛ፡- መወሰን ከባድ ነው፡፡ ዝም ብለህ ያገኘኸውን ከመስራት በተቻለ መጠን፣ የተለያዩ ገፀ ባህሪያት በመምረጥ መስራት የተሻለ ይመስለኛል፡፡ ገደቡን ግን ሁሉም ሰው አቅሙን ታሳቢ በማድረግ ነው የሚወስነው፡፡ እኔ ጥሩ ታሪክ ካገኘሁ ሙያውን የምወደው ስለሆነ ጊዜዎቼን አጣብቤ መስራት እችላለሁ፡፡ ነገር ግን ይሄን ያህል ብሎ ቁጥር ማስቀመጥ አይቻልም፡፡ በተደጋጋሚ ተመሳሳይ ፊት በፊልም ውስጥ መመልከታችን ብዙ ሰው ስሌለን ነው፡፡

ጥያቄ፡- ወደ ፊልም ስራ ስትገቢ የቤተሰብ ጫና አልነበረብሽም?

አዚዛ፡- በጣም ነበረብኝ፡፡ በተለይ አባቴ ደስተኛ አልነበረም አሁንም፡፡ ምናልባት ወደፊት በስራዎቼ ማሳመን ሳይኖርብኝ አይቀርም፡፡ ቀሪ ቤተሰቦቼ ግን ስራዬን ይወዱልኛል ያበረታቱኛል፡፡

ጥያቄ፡- ወደፊት በፊልም ኢንዱስትሪው ላይ ምን አይነት ተፅዕኖ የመፍጠር ዕቅድ አለሽ?

አዚዛ፡- አቅሙ ቢኖረኝ እና የፊልሙን ኢንዱስትሪ በሁሉም ዘርፍ ማሳደግ ብችል፣ አሻራዬን ጥዬ ባልፍ እመኛለሁ፡፡ እንደ ብዙዎቹ ባለሙያዎች፡፡ ትልልቆቹ ሆሊውድ እና ቦሊውድ የመሰሉ የፊልም ኢንዱስትሪዎች ከምንም ተነስተው ነው ዛሬ የሁሉንም ዓይን መግዛት የቻሉት፡፡ ቀደም ሲል እነዚሁ ኢንዱስትሪዎች እኮ ብዙ የሚተቹና እንከን የሞላባቸው የፊልም ስራዎችን ሲያመርቱ መቆየታቸው መዘንጋት የለበትም፡፡ እኛም በዚሁ መንገድ አንድ ቀን ከምንፈልገው ደረጃ ላይ እንደምንደርስ እምነት አለኝ፡፡ የዚህ ጉዞ አካል መሆን ደግሞ እፈልጋለሁ፡፡

ጥያቄ፡- ተመልካቹ አሁንም የፊልም ባለሙያውን እየመራው ነው ብለሽ አታምኚም?

አዚዛ፡- ነበር ብል ይሻለኛል፡፡ ምክንያቱም ያንን አካሄድ ሰብረው የወጡ ፊልሞችን መመልከት እየቻልን ነው፡፡ በአንድ ወቅት የኮሜዲ ስራዎች ብቻ ነበር በተመልካቹ የሚመረጡት፡፡ ነገር ግን እንደ ረቡኒ፣ ቀሚስ የለበስኩ ለታ፣ የሎሚ ሽታ እኔም የተወንኩበት ሰኔ 30ን ስትመለከት፣ በሌላ አቅጣጫ የቀረቡ ስለሆነ አሁን ላይ የፊልም ኢንዱስትሪው ተመልካቹን መምራት ጀምሯል ማለት ያስደፍራል፡፡

ጥያቄ፡- መለከት ተከታታይ የቴሌቪዥን ድራማ ላይ በመሪ ተዋናይነት እሰራሽ ነው፣ ገጸባሃሪዋ ድራማውም ተስማምተውሻል?

አዚዛ፡- በጣም ደስ የሚል ድራማ ነው፡፡ የእኔ ታሪክ  ባይሆንም በእውነተኛው ዓለም እየኖርኩት ያለውን ህይወት ነው ድራማው ላይ እየሰራሁ ያለሁት፡፡ አዚዛ ዋና ህይወት አላት፣ ከዛ በተረፈ ደግሞ አርቲስት ናት፣ ያንን ድራማ ውስጥ እያየሁት ስለሆነ በጣም ደስ ይለኛል፡፡ አብረውኝ የሚሰሩት ተዋንያንም ብዙ እንድተጋ የሚያደርጉኝ ሰዎች ስለሆኑ ተመችቶኛል፡፡

ጥያቄ፡- በቅርቡ በልዩ ሁኔታ ቀለበት አስረሻል፣ ወደ አዲስ ህይወት ለመግባት እየተዘጋጀሽ ነው ምን ይመስላል ዝግጅት?

አዚዛ፡- ሄሎም ይባላል ጓደኛዬ… ለረዥም ዓመታት በጓደኝነት አብሮኝ የነበረ ሰው ነው፡፡ በቅርቡ በሰርግ ለመጋባት እየተዘጋጀን ነው፡፡ በጣም ደስተኛ ነኝ፡፡

ጥያቄ፡- አዚዛ ምን አይነት ባህሪ ነው ያላት? ቁጡናት ይሉሻላ?

አዚዛ፡- አንተ ነህ ያልከው፡፡ አዚዛ እንዲሁ በመሳቅ ነው የምትታወቀው፡፡ እንደውም ካልሰማህ ከአባይ በኋላ በሳቅ ውስጥ የሚገኘው የአዚዛ እምባ ነው የሚገደበው ተብሏል፡፡

ጥያቄ፡- ተስፋ የምትጥይባት ተዋናይ አለች?

አዚዛ፡- አዚዛ አህመድ (ረዥም ሳቅ) ራሴ ላይ ተስፋ ብጥል ምን ክፋት አለው?

ጥያቄ፡- ምንም ክፋት የለበትም እሱስ፡፡ መብቴ ፊልሞች ላይ እንዲሳካልኝ አስተዋፅኦ አድርጎልኛል ብለሽ ታስቢያለሽ?

አዚዛ፡- አይመስለኝም፡፡ አዚዛን ለፊልም ስራ ሲመርጧት በውበቷ ነው ብዬ አላስብም፡፡ የሚመረጡ ሰዎች ውበት አንዱ መለኪያቸው ሊሆን ይችላል፡፡ ከዛ በተረፈ ግን መስራት ትችላለች ብለው ያስቡበት ቦታ ላይ ካስት እንደሚያደርጉኝ ነው የማውቀው፡፡

ጥያቄ፡- በፕሮዲውሰርነት መሳተፍሽ ነግረሽል ፊልም የማዘጋጀት ፍላጎቱ አለሽ?

አዚዛ፡- ዝም ብሎ ሁሉንም መነካካት እንዲሆንብኝ አልፈልግም፡፡ እኔ ዳይሬክት ባደርጋቸው ብዬ ያዘጋጀኋቸው ስራዎች አሉኝ፡፡ ነገር ግን በደንብ ጎበዝ ሆኜ ካልሆነ በቀር ነካክቼ ብቻ ማለፍ አልፈልግም፡፡ ስለዚህ የተወሰኑ ጊዜዎችን በትወናው መቆየት እመርጣለሁ፡፡

ጥያቄ፡- ተሰጥኦው የሌላቸው ሰዎች የጥበብ ስራ ውስጥ መግባታቸው ችግር የለውም?

አዚዛ፡- ፊልም ወይም ድራማ ለመስራት ገንዘብ ማውጣት ብቻውን በቂ ነው ብለው የሚያስቡ ሰዎች፣ ከዛ በተረፈ ከሰዎች ጋር ባላቸው ቀረቤታም ፊልም ወይም ድራማ መስራት ቀላል የሚመስላቸው የሉም ማለት አይቻልም፡፡ እነዚህ ሰዎች ከትንሽ ጊዜ በኋላ ኢንዱስትሪው ውስጥ አናያቸውም፡፡ ይሄ ደግሞ ራሱን መሰረት ያስያዘ ባለሙያ እንዳንመለከት ምክንያት ሊሆን ስለሚችል ችግር ይሆናል፡፡

ጥያቄ፡- በምህንድስናው ሙያሽ ትሰሪበታለሽ?

አዚዛ፡- ወደፊት፡፡ ምክንያቱም ብዙ ለፍቼበታለሁ፡፡ እንደውም በቅርብ ጊዜ ሁለተኛ ዲግሪ የመቀጠል ፍላጎት አለኝ፡፡

ጥያቄ፡- ስክሪፕት ትመርጫለሽ?

አዚዛ፡- ተመሳሳይ የሆኑ ገፀ ባህሪያት ላይ መስራት ስለማልፈልግ በተቻለ መጠን እመርጣለሁ፡፡ ትላንት ሰኔ 30 ላይ የታየችውን አዚዛ ሌላ ፊልም ላይ መድገም አልፈልግም፡፡ ከዛ ባለፈ ግን የፀሐፊው ማንነት ለእኔ ቦታ የለውም ጥሩ ስራ እስከሆነ ድረስ፡፡

ጥያቄ፡- አመሰግናለሁ፡፡

The post ‹‹በእውነተኛው ዓለም እየኖርኩት ያለውን ህይወት ነው ድራማው ላይ እየሰራሁ ያለሁት›› ተዋናይትና ሲቪል ኢንጂነር አዚዛ አህመድ appeared first on Zehabesha Amharic.


እድገቱ ለማነው? “አስደናቂ እድገት ወይንስ ተከታታይ ድህነት” –ዶር አክሎግ ቢራራ

$
0
0

ክፍል ሶስት

Dr Aklog Birara

ዶር አክሎግ ቢራራ

ድሃ፤ ኋላ ቀር፤ የእርዳታ ጥገኛ በሆነችው ኢትዮጵያ የፓርቲና የመንግሥት ባለሥልጣናት የድሎት ኑሮ አሰቃቂውን የሕዝብ ኑሮ አያንፀባርቅም። የዚህ ሃተታ መሰረት የአሁኑ የእድገት ውጤት የገቢና የኃብት የተዛባ ስርጭት ከቀጠለ ለብዙ ተከታታይ ትውልዶች የተዛባ ኑሮ፤ አለመረጋጋት፤ ጥልቀት ያለው ድህነት፤ አስፈላጊ ያልሆነ የተፈጥሮ ኃብት ይገባኛልነትና ከእነዚህ ጋር የተያያዘ የእርስ በርስ ግጭትና ከአሁኑ የባሰ ስደት ይፈጥራል የሚል ነው። የማንኛውም የበለፀገና በማደግ ላይ የሚገኝ አገር መንግሥት ትኩረት ለተወሰኑ ባለ ኃብቶች ተጨማሪ ገቢና ኃብት ለማበርከት አይደለም። ጥረት የሚያደርጉት በተቻለ መጠን የአብዛኛው ሕዝብ ገቢ እንዲጨምርና (ፍትህ የሚባለው)፤ የአብዛኛው ሕዝብ ኑሮ እንዲሻሻል ነው። ምን ማለት ነውና ለምን? በቀላል አነጋገር፤ ገቢ ጨመረ፤ ኑሮ ተሻሻለ ሲባል ዋናው መስፈርት የአብዛኛው ሕዝብ ህይወትና ኑሮ ተሻሻለ ማለት ነው። ይኼን ለማድረግ የሚቻለው የኢኮኖሚው መርህ ሕዝብን መአከል (People-centered) ያደረገ ሲሆንና ለሕዝብ ታዛዥነት ያለው የፖለቲካ አመራር (People-anchored governance) ሲኖር ነው። ======[ሙሉውን ለማንበብ እዚህ ይጫኑ]======

The post እድገቱ ለማነው? “አስደናቂ እድገት ወይንስ ተከታታይ ድህነት” – ዶር አክሎግ ቢራራ appeared first on Zehabesha Amharic.

ይድረስ ለአቶ በቀለ ገርባ ፣ለአቶ ጁሃር መሀመድ እና አጋሮቻችሁ  ለመተባበር መተማመን ይቅደም!

$
0
0

Olf-flagምንም እንኳን እኔ የአማራዉ፣ የኦሮሞዉ፣ የትግሬዉ ፣ተወላጅ ባልሆንም  እንደ ኢትዮጵያዊነቴ የኦሮሞ ምሁራን ለአማራዉ የአቀረቡት የትብብር ጥያቄ ልቤን ሰለነካዉ ለዉጤቱ ስምርት የሚስማኝን ለመግለጽ ነዉ፡፡

ወያኔ ወደ በረሃ የገባሁት አማራን እና የክርስትናን ሃይማኖትን አጥፍቼ ኢት ጵያን ለማፍረስ ነዉብሎ አቅዶ እና በፕሮግራም ነድፎ እየሠራበት መሆኑን ኢትጵያዊዉ ሁሉ የሚያዉቁት ሐቅ ነዉ ፡፡

ወያኔ በእቅዱ መሠረት አየአጠፋዉ ያለዉ አማራዉን ቢሆንም በአጠቃላይ ኢትዮጵያዊዉን እየጎዳ መሆኑ ለማንም ግልፅ ነዉ፡፡ ሁሉም ኢትዮጵያዊ ልብ ሊለዉ የሚገባዉ ወያኔ አማራን ለማጥፋት በኦሮሞ ጀርባ ተጠልሎ የሌላዉን ብሔረሰብ እና የአማራዉን ሆድ አደሮቸ  እጀታ፤ ሕዝቡን መጥረቢያ አድርጎ በመጠቀም የአማራዉ ሕዝብ ከኢትዮጵያ ምድር ላይ እንዲጠፋ እየተሠራ መሆኑን በዓይናችን እየአንነዉ፡፡ ለዚህም መረጃ የሚሆነዉ፤

1.በ1980 ዓ ም በወለጋ አሶሳ አዉራጃ ባምቤሊ ወረዳ ሸርቆሌ ከትምህርት ቤት ዉስጥ አሽጎ ከ400 በላይ አማራ በሳት መጋየቱ፤

2.በ1982 ዓ ም በወለጋ አሶሳ ከ500በላይ አማራ በሳት መጋየቱ፤

3.ከ1992 እስከ1993 ዓ ም ኦሕዴድ የኦሮሞን ሕዝብ በመቀስቀስ በገጀራ በጥይት አማረዉ መጨፍጨፉ፤

4 በ2001 በበደኖ ወረዳ በብዙ ሽህየሚቆጠሩ አማሮች መገደላቸዉና  መባረራቸዉ፤

5.በ2006 በምዕራብ ሸዋ ዞንአምቦ ወረዳ በኦሕዴድ ካደሬዎች በብዙ ሽህ የሚቆጠሩ አማሮች መገደል እና መባረር፤

  1. በ2006ዓ ወለጋ በጊምቢና በቄለም አዉራጃ በሽህ የሚቆጠሩ አማሮች መገደልና ከ8ሽህ በላይ ከመኖሪያ ቦታቸው መፈናቀላቸዉ ፤ ለዚህም ግንባርቀደም የኦሮሞ ተወናዋኞች አቶ ሽፈራዉ ሽጉጤ፡ አቶ ዘዉዱ እንዳለ: እንስፔክተር ኃይሉ ድሪባ፡ አቶ ጋሻየ ገቼ ፡መቶ አለቃ ገነነ በየነ ወዘተ ናቸዉ፡፡

ኦሮሞች ከአማራ ጋር ተባብሮ አሁን እየጨፈጨፈአችሁ ያለዉን ወያኔን ማጥፋት ሲገባችሁ የኦነግናሌሎች የኦሮሞ ድርጅቶች አምራር  የወያኔን ኑሮ ለማራዘም የወያኔን ሃሳብ በመቀበልና ያለመዉን ለማሰፈጸም ተባብራቸኋል፡፡ ለዚህም መረጃ የሚሆነዉ አሮሞዉ ከአማራዉጋር ተባብሮ ለመኖር ሳይሆን  መነጣጠልን  ከትዉልድ ወደትዉልድ ለማስተላለፍ በቃል ከሚነገረዉ በጽሁፍ ከሚጻፈዉ አልፎ የአኖሌን ሃዉልት በመትከል በናታቸዉ ጉራጌ የሆኑትን አጼምኒልክ ያልሠሩትን   እንደሠሩና የአማራ ብቻ ተወላጅ እንደሆኑ አድርጎ በመቀስቀስ ለወያኔ ተባባሪነታችሁን አረጋግጣችኋል፡፡ ከዚያም በመቀጠል አቶ ጁሃር መሀመድ አማራ ማለት ክርስቲያን ነዉ በሚል የኦሮሞ ክርስቲያኖቸን ጨምሮ ክረስቲያን በመሆናቸዉ ለማጥፋት አማራን አንገቱን እቆርጣለሁ የሚለ መፈክር አሰምቷል ፤ አቶበቀለ ገርባም አማራ በኦሮሞ ሕዝብ ላይ ያደረሰዉ  በደል አብሮለመኖር አያስችልም ሲሉ ተሰምተዋል፤

አሁን ደግሞ ወያኔን ለማጥፋት ከአማራዉ ጋር መተባበር ያስፈልጋል ፤ስለ አንዲት ኢትዮጵያ ማሰብ ፣አለብን በማለት ተባብሮ ወያኔን ማጥፋት  እንዳለብን ጥሪአቅርባችኋል፤ የምትሉት  እዉነት ከሆነ እሰየዉ የሚያሰኝ ነዉ፡፡ መተባበርን የሚጠላ ከወያኔ በስተቀር ያለ አይመስለኝም፤ ነገሩም ሀቅ ነዉ፡፡ ወያኔ የጎዳ ሁሉንም ኢትዮጵያዊ እንጂ አማራን ብቻ አይደለም የሚሉ፤ የአማራዉን ጉዳት በማቃለል  አማራዉ ችግርን ተደራጅቶ  እንዳይታገል ለጥቃት ተጋላጭ እንዲሆን የሚጥሩ የወያኔ አጋሮች እንዳሉ የታወቃል፤እያንዳንዱ ኅሊና ያለዉ ሰባዊ ፍጡር ሁሉ ሚዛናዊ ፍርድ ለመስጠት ያስችል ዘንድ በአማራዉ ሕዝብ ላይ እና በሌላዉ  ነገድ ላይ የተፈጸመዉን  በደል አነጻጽረን እንይ ፤

1.ወያኔ አንደኛ ጠላቴ አማራነዉ፤ የወነበድኩተም አማራን ለማጥፋት ነዉ ብሎ በፕሮግራም ነድፎ ለማጥፋት አልሞ ሲነሳ በሌላዉ አላልመም፤ ለዚህ ማረጋግጫ ማነፌቶዉን ማንበብ ነዉ፡፡

2.አማራዉ በኢትዮጵያ እኔ ከምሰጥህ ዉጭ አትኖረም ተብሎ በአንድ ጊዜ ከጉራፈርዳ  ወረዳ ብቻ  ከሰባ ሽህ ሕዝበ በላይ ሲባረር፤ ለሃያአምሰት አመታት በሽህ የሚቆጠር አማራ ሲገደል ሲገረፍ ፤ንብረቱን ሲዘረፍ ሲባረር በሌላዉ ብሔረሰብ ላይ ይህ አልተፍጸመም፡፡

3.የአማራዉን ከልል ለም መሬት የሆኑትን ከአምስት በላይ ወረዳዎችን ለራሱ ሲወስድ በሌላዉ ይህ አልተፈጸመም፤

  1. በአማራዉክልል

ሀ. የወላድ ማምከኛ የወሊድ መቆጣጠሪያ ነዉ ተብሎ   ለወላድ ሴቶች ተሰጥቶ ትውልዱየለሸ ሆኗል፤

ለ. ቀኑ ያለፈበት የማይሠራ መድኃኒት ለሃያ አምስት ዓመታት ያለማቋረጥ ታድሏል በሌላዉ ይህ አለትፈጸመም ፤                  ሐ. የኤድስቫይረስ በመርፌ ሆን ተብሎ ለዐማራው ሲሰጥ  በሌላዉ  ይህ አልተፈጸመም.

መ. አማራዉን የማጥፋት ዘመቻ በድል እያአጠናቀቁ ለመሆናቸዉ መለስ ዜናዊ፤ ሳሞራ የኑስ. ስብሃት ነጋ በፌስታና በኩራት እየተንጎራደዱ አማራን እነዳይነሳ አድርገን ገድለን ቀብረነዋል፤ አከርካሪዉን ሰብረነዋል በማለት የአገሪቱ መሪዎች አረጋግጠዋል ፤ በሌላዉ ይህ አለተፈጸመም፤አልተነገረም፡፡

ሠ. በ1999 ዓም በተደረገው የሕዝብ ቆጠራ የአማራዉ ሕዝብ ቁጥር በ2.5 ሚሊዮንቀንሶ  በመገኘቱ ምክንያቱ ምንድን ነዉ ተብሎ መለስ  ሲጠየቅ፤ በፈገግታ ደስታዉን በመግለጽ ‹በኤድሰ ያለቀ ነዉ› በማለት አረጋግጧል ፤ በልላዉ ይህ አልተፈጸመም፤ ማረጋገጫም አልተሰጠም፤ይህ ከላይ ከ ‹ሀ› እስከ ‹ሠ› የተዘረዘረዉ በአማራው ላይ ብቻ የተፈጸመ የዘር ማጥፋትና  የዘር ማጽዳት ወንጀል ለመፈጸሙ አገሪቷን እየመራን ነዉ የሚሉት ቁነጮ ምሪዎች አፋቸዉን ሞለተዉ የመሰከሩለት ነዉ፡፡ መለስ አማራ ማለት ኢተዮጵያ፤  ኢትዮጵያ ማለት አማራ ነዉ ፤ በሚል ቁንጽል አስተሳሰቡ መነሻነት አማረን ለማጥፋት ሌላዉን ብሄረሰብ አደራጅቶ ማዘመት ብሎ በአማራዉ ላይ አዘመተ፤ በዚህም በኦነግ እና ኦሕዴድ ፈታዉራሪነት የአማራዉ እለቂት እና በሌላዉ ብሔረሰብ የመጠላት ዉጤት አያሳየ ሲመጣ እቀዱ ለመፈጸሙ ደስታዉን እነዲህሲል ገለጸ፤  ‹አማራዎች ሲመነጠሩ ሌላዉ ኢትዮጵያዊ የሚቆጣዉ ኢትዮጵያን የማፍረሱ ዓላማ ሲፈጸም ወለል ብሎ ሰለታያቸዉ እንጂ፤ አማራ ስለሆኑና ለአማራዉ አድልተዉ እንዳልሆነ አማራዉ ይረዳል› መለስ ዜናዊበማልት የሱን እቅድ ዉጤት አጠቃሎ መግለጡ ይታወሳል፤  በተጨማሪም አማራዉ በኢተዮጰያዊነቱ አንደማንኛዉም ኢትዮጵያዊ በደልተፈጽሞበታል፡፡ የኦሮሞ ሕዝብ ወኪል ነን የምትሉ ሁሉ ከአማራ ጋር የእንተባበር ጥሪ ስታስተላልፉ  ለመተባበር መተማመን  ቅደሚያ ሊሰጠዉ ይገባል፤ ይህ ካልሆነ በአሳለፍነዉ ዘመን ወሰጥ እንተባበር እና ተባብረናል የሚሉ ቃላት ቢያንስ ከአምሳ ጊዜ በላይ ተነግረዋል፤ በየሳልስቱም ተሰባብረዋል፡፡ ወያኔም  ለዚህ ቋንቋ ጀሮ ጠገብ ሆኗል፤ ስለዚህ ከአማራ ጋር እንተባበር የምትሉ የኦሮሞ ምሁራን ከልባችሁ ከሆነ በተግባር ለመፈጸም ያስችላችሁ ዘንድ፤ አማራዉ ከናንተ ቢያንስ ለተፈጸመበት በደል የእምነት ቃል ይፈልጋል፤  ካልሆነ አማራዉ እነዴት ሊያምን ይችላል?  ምክንያቱም እናንተ እንትባበር እያላችሁ በንግግራችሁ ጎን ለጎን ታህሳስ 3ቀን 2015  በምዕራብ  ሸዋ ዞን አማራዎች ሴቶች ጡታቸዉን ወንዶች ብልታቸዉን   በፒንሳ  እየተጠመዘዘ የቁም ስቃይ እያዩ ተገድለዋል፤ ተባረዋል፤ ለኦሮሞ ትብብር ፈላጊ ምሁራን አማራዉ ከሁሉ በበለጠ በሱ ላይ የተፈጸመዉን ጉዳት እርም ብሎ በመተዉ ሊተባበር የሚችለዉና በመተባበር ወያኔን ለመጣል የሚሰለፈዉ  በናንተ በኩል የሚከተሉት ሀሳቦች በእምነትና በሀዘን ሲቀርቡለት ነዉ፡፡

ሀ. በወያኔ ዘመን በማወቅም ሆነ ባለማወቅ አማራን ለማጥፋት ከወያኔ ጋር አጋር ሁናችሁ መቆየታችሁን                            ለ. በአማራዉ ላይ ከሌላዉ ብሄረሰብ በተለየ የዘረማጥፋት እና የዘር ማጽዳት ዘመቻ በወያኔ የተፈጸመበት መሆኑን ሐ.ከእነግዲህ በወየኔ አስተባባሪነት በቅጥረኛ ኦሮሞዎች ታዘዉ አማራን የየሚያጠፉትን የአማራዉ ጠላት ጠላቴ ነዉ ብላችሁ የወያኔ ባንዳ የሚሆኑትን ኦሮሞዎች እያጋለጣችሁ ለሌላዉ ብሄረሰብ በማሳወቅ ከናንተ ዉጭ መሆናቸዉን የምታጋለጡ መሆናችሁን ፤የአሰባችሁትንና ዓላማችሁን በመጨመር መግለጫ  ብታወጡ አማራዉጥሪያችሁን በደስታ ይቀበለዋል የሚል ዕመነት አለኝ፤  ካለሆነ ግን አማራዉ የሚተርተዉ ተረት አለ፤ አሱም ‹የጠገብ ጂብ ሰድጄ፤ የተራበጅብ አልተካም› የሚል፤

ከመግለጫዉ በተጨማሪ የወያኔ ተቃዋሚ ነኝ የሚሉትን የአማራ ምሁራን፤ የአማራዉን ንቅናቄ ኃይል  የሲቪከ ድርጅት ወዘተ ጠርቶ በጋራ ዉይይት ማካሄዱ መተማመንን ይፈጥራል የሚል ዕምነት አለኝ፤ ስለዚህ የሰከረዉ ዓሣ ወያኔ ሳመልጣችሁ ተግባራዊ እነድታደርጉ የአማራዉምሁራን ንቅናቄወችና ድርጅቶች ለጥሪያአቸዉ ቀናና ፈጣን መላስ ሰጥችሁ በወያኔ ላይ በሁሉም ክልለና ቦታ  ዘመቻ በማካሄድ የሠፊዉን ሕዝብ ቀንበር  ሰባብራችሁ እንደምት ጥሉት   ተስፋ አለኝ፡፡ ከተስፈኞቹ አንዱ

The post ይድረስ ለአቶ በቀለ ገርባ ፣ለአቶ ጁሃር መሀመድ እና አጋሮቻችሁ  ለመተባበር መተማመን ይቅደም! appeared first on Zehabesha Amharic.

“ መሬት እግር አለው ይሄዳል እንደሰው—“ –በስደት የኢትዮጵያ መምህራን ማህበር አባላት አስተባባሪ ኮሚቴ የተሰጠ መግለጫ

$
0
0

teachers-associationየሰው ልጅ ሕይወቱ ከመሬት ጋር በእጅጉ የተቆራኘ ነው።ለዚህም ነው ሕዝቦች ለም መሬት ለማግኘት በግጭት ሲራኮቱ የቆዩት። ለቅኝ ግዛት ታሪካዊ አነሳስም ዋነኛ ሰበቡ ይኸው የመሬት ጉዳይ ነው። ኢትዮጵያ አገራችን ከወራሪዎች ራሷን በመከላከል ዳር ድንበሯን አስጠብቃ የመኖሯ ትርጉም የዜጎች የመሬት ባላቤትነት ዕምነታቸው የፀና ስለነበር እንደሆነ ዕሙን ነው። አያት ቅድመ አያቶቻችን ስለመሬት ያላቸው ግንዛቤ ጥልቀትና ምጥቀት ያለው ነበር። አገር፣ ዳርድንበር፣ መሬትን ለመጠበቅ ማንኛውንም መሰዋዕትነት እየከፈሉ ያለፉትም በዚህ ግንዛቤና ዓላማ ላይ ተመስርተው ነው።ምሳሌያዊ ንግግራቸው ፣ ተረቶቻቸው፣—

[ሙሉውን መግለጫ ለማንበብ እዚህ ይጫኑ]—

The post “ መሬት እግር አለው ይሄዳል እንደሰው—“ – በስደት የኢትዮጵያ መምህራን ማህበር አባላት አስተባባሪ ኮሚቴ የተሰጠ መግለጫ appeared first on Zehabesha Amharic.

በኦሮሚያ ከተካሔደው የተቃውሞ ምክንያቶች ጋር የተያያዙ አዳዲስ መረጃዎች እየወጡ ነው |አለምነህ ዋሴ ያነበዋል

ኤፍሬም ታምሩ ከ34 ዓመት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ የሰጠው ቃለ-ምልልስ |“ምንም ሳይጎልብኝ በጉርምስና ነው ከሃገር የወጣሁት”| Video

$
0
0

በሙዚቃው ዓለም በቆየባቸው ዓመታት ውስጥ ለመጀመሪያ ከ34 ዓመት በኋላ ከሰይፉ ፋንታሁን ጋር ቃለምልልስ ያደረገው ኤፍሬም ታምሩ በአሁኑ ወቅት ኑሮውን አዲስ አበባም አሜሪካም ማድረጉን እና በወቅቱ ከሃገር የወጣበትን ምክንያት ሲጠየቅም “ምንም ሳይጎልብኝ በጉርምስና ነው ከሃገር የወጣሁት” ሲል በተደጋጋሚ በቃለምልልሱ ጣልቃ እያስገባ ተናግሯል:: ድምፃዊው በመኖሪያ ቤቱ ያደረገውን ቃለምልልስ በሁለት ቭዲዮ አስተናግደናል – ያድምጡት::

ክፍል 2 ቃለምልልሱ ከፎቶው በታች ቀርቧል
ephrem Tamiru 2015

The post ኤፍሬም ታምሩ ከ34 ዓመት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ የሰጠው ቃለ-ምልልስ | “ምንም ሳይጎልብኝ በጉርምስና ነው ከሃገር የወጣሁት” | Video appeared first on Zehabesha Amharic.

መሬት ለአራሹ!

$
0
0

ገለታው ዘለቀ

በኣስራ ዘጠኝ ስልሳዎቹ ኢትዮጵያ ደምቃ ነበር። የለውጥ ጥም ይዟት ትጮህ ነበር። መቼም በየሃገሩ ኣገራዊ ችግሮችን መልክ ኣስይዞ፣ መሪቃል ወይም መፈክር ኣውጥቶ ለውጡን የሚመራውና የለውጥ ሃይል የሆነው ወጣቱ ሲሆን በተለይ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ሁሌም ቀዳሚዎች ናቸው። ታዲያ በዚያ የለውጥ ወራት ጊዜ ከነበረው ኣንዱና ትልቁ ጥያቄ የመሬት ላራሹ ጉዳይ ነበር ኣሉ።
abebe Gelaw

መሬት ላራሹ! መሬት ላራሹ! መሬት ላራሹ!………

ወጣቱ ድምጹን ኣሰማ ። ኣራሹ ማን ነው? ያውጭሰኛውና መሬት የለሹ ዜጋ ነዋ። በጥቂት የመሬት ከበርቴዎች እየተጨቆነ የሚኖረው የሰፊው ድሃ ህዝብ ግፍ ይብቃ፣ ኣዲስ ዘመን መጥቷልና እናንተ የመሬት ከበርቴዎች ሆይ በቃችሁ። ኣራሹ ገበሬ እጣው በሆነችው በዚህች ኣገር ውስጥ፣ የርስቱ ገመድ በወደቀባት በዚህች ምድር ላይ መሬት ይኑረው ነው ጥያቄው። በርግጥ ይህ ጥያቄ በጥሩና ሳይንሳዊ በሆነ ሁኔታ የተቀመጠ ይመስለኛል።

በተለምዶ ያ ትውልድ የምንለው ከንጉሱና ከፊውዳሉ ጋር ሳይሰለች ታገለ። ለገበሬው ኣባቱ ድምጽ ሆነለት። በርግጥ ትግሉ የመሬት ላራሹ ጉዳይ ብቻ ሳይሆን ኣጠቃላይ የኢትዮጵያን ሶሺዩ ፖለቲካ የሚመለከት ሰፊ የለውጥ ትግል ነበር። ይህ ጥያቄ እንደቀጠለ ብዙ ቆየና በ 1966 ዓ.ም ለውጥ ድንገት ፈነዳ። ሲፈነዳ ባልተጠበቀ መንገድ ነበርና ብዙ ለውጥ ፈላጊ ተማሪዎችን ኣላስደሰተም። ወታደር ስላፈነዳው በኣገሪቱ ስጋቶች ኣየሉ። ይሁን እንጂ ደርጉ ስልጣኑን በያዘ በማግስቱ የተማሪውን ጥያቄ “መሬት ላራሹን” እመልሳለሁ ኣለ። የካቲት 25 ቀን 1967 ዓ.ም ኣንድ ስር ነቀል ኣዋጅ ታወጀ። መሬት የሰፊው ህዝብ ነው ተባለ። በመሰረቱ ይሄ ሰፊው ህዝብ የሚባል ነገር በውስጡ ሌላ ኣነስተኛ ህዝብን ያገለለ ይመስላል። በርግጥም በሶሻሊስቶች ትግል ውስጥ የመደብ ትግል ዋናው ነገር ስለሆነ ታጋዮች ለሰፊው ህዝብ ሲሉ ሊበቀሉት የተነሱት ኣነስተኛ የተባለ መደብ ስላለ ነው። ይህ ግን ኣደገኛ ነው። ትግል ለሁሉም ነጻነት፣ ለዜጎች ሁሉ ሲሆን ነው ክብ ከሆነ ጭቆና የሚወጣው። ይህ ኣዋጅ በወቅቱ ጭቁን ለተባለው መደብ ከፍተኛ ለውጥ ነበር። መሬት የሌላቸውን ባለመሬት ያደረገ፣ ከፊውዳል ጭሰኝነት ያላቀቀ ታሪካዊ ለውጥ ነው። ይሁን እንጂ ታዲያ የመሬት ላራሹ ጥያቄ ሙሉ በሙሉ ተመለሰ ማለት ኣይቻልም። የመሬት ላራሹ ጥያቄ የገበሬውን የባለቤትነት ጥያቄ የሚመለከት ነው። ደርግ ከፊውዳሉ ነጥቆ ባለቤትነቱን ለህዝብ ነው የሰጠሁት ኣለ። ይሁን እንጂ ህዝብ የመሬት ባለቤት ነው ለማለት በሆነ መንገድ ተደራጅቶ መምጣት ኣለበት። ይህ ግዙፍ ማንነቱ ደግሞ በመንግስት ነው የሚገለጸው። መንግስት ሲስተም ስላለው በተግባር የሆነ ሃብት ባለቤት ሊሆን ይችላል። በመሆኑም በተዘዋዋሪ መሬት የመንግስት ነው እንደማለት ነው የደርግ ኣዋጅ። በርግጥ ይህ የመሬት ባለቤት የሆነው መንግስት ለጭቁኑ ለሰፊው ህዝብ የቆመ በመሆኑ የሃገሪቱን መሬት በገመድ እኩል እኩል ኣካፍሏል። ከዚህ በፊት በፊውዳሉ ስርዓት ውስጡ የበገነው ሰፊ ህዝብ በዚህ ኣዋጅ ለስሜቱ ርካታ ቢያገኝም ሁሉም እኩል እኩል በመካፈሉ ብዙ ድሆችን ቢያደስትም ኣጠቃላይ ኣገራዊ የኢኮኖሚ ተጽእኖው ግን ግራና ቀኝ ኣልተጠናም። የሆነ ሆኖ መሬትን መንግስት ይዞ ኣስራ ሰባት ኣመት ከዘለቅን በሁዋላ ወያኔ መራሹ መንግስት በግንቦት ወር 1983 ዓ.ም ኣዲስ ኣበባን ተቆጣጠረ። ህወሃት ለሰፊው ህዝብ ጥቅም ሲባል በረሃ እንደገባ ኣሁንም ለሰፊው ህዝብ ጥቅም ሲል መንግስትን እንደተቆጣጠረ ኣዲስ ኣበባ ላይ ገለጸ። ያ የተንጠለጠለው የመሬት ላራሹ ጥያቄ ምን ይሆን ይሆን እየተባለ ሲጠበቅ ይህ መንግስት ደግሞ በህገ-መንግስቱ ላይ እንዲህ ሲል ኣወጀ።

ኣንቀጽ 40

3. የገጠርም ሆነ የከተማ መሬትና የተፈጥሮ ሃብት ባለቤትነት መብት የመንግስትና የህዝብ ብቻ ነው።
መሬት የማይሸጥ የማይለወጥ የኢትዮጵያ ብሄሮች ብሄረሰቦችና ህዝቦች የጋራ ንብረት ነው።
4. የኢትዮጵያ ኣርሶ ኣደሮች መሬት በነጻ የማግኘትና ከመሬታቸው ያለመነቀል መብታቸው የተከበረ ነው

ይህ ኣዋጅ ከየካቲቱ በምን ይለያል? ካልን መሬት የህዝብ ብቻ ሳይሆን የመንግስትም ሃብት ነው የሚል በመሆኑ ነው። ይህንን ጽሁፍ ለማዘጋጀት ከመነሳቴ በፊት ኤንጂነር ይልቃል ጌትነትና ዶክተር በያን ኣሶባ ለቪኦኤ የሰጡትን ቃለ ምልልስ ኣዳምጨ ነበር። ሁለቱም መሳጭ የሆነ መልእክት ኣስተላልፈዋል። ኤንጂነር ይልቃል ስለ መሬት ባለቤትነት ሲናገሩ በሚገባ ገልጸውታል። ህወሃት መራሹ መንግስት መሬት የህዝብና የመንግስት ነው ሲለን ከፍ ሲል እንዳልነው በተግባር ህዝብ የመሬት ባለቤት የሚሆነው በመንግስት በኩል ነው። ከደርጉ የተለየ የመሬት ኣዋጅ የለም ለማለት ነው።

ኣንድ ፖሊሲ ወይም ህግ ሲወጣ ከሁሉ በላይ ቶሎ የሚማርከኝ የፍልስፍናው መነሻዎች ወይም መሰረቶች ናቸው። በዚህ በጣም እሳባለሁ። እንዲገባኝም የምፈልገው ያ ነው። መሬት የመንግስትና የህዝብ ነው ብሎ ኣረፍተ ነገር ማራዘሙ ከደርግ የተሻለ የመሬት ህግ ኣለ ኣያስብለውም። ከመነሻው መሬት የህዝብ ነው የሚለው ኣባባል ራሱ ችግር ኣለበት። በመሰረቱ መሬት ኣይደለም የህዝብ መባል ያለበት። ኣገር ነው የህዝብ መባል ያለበት። መሬት ግን የግል ነው መሆን ያለበት። መሬት የዜጎች ነው መሆን ያለበት። ኣገር ነው የወል እንጂ መሬት በዜግነታችን እየተዘረዘረ የሚደርሰን የእግዚኣብሄር ጸጋችን ነው።

ሁለተኛው ሳቢ ጉዳይ ደግሞ በጣም የተለየ ኣስገራሚ የፍልስፍና መሰረት ያለው ጉዳይ ሲሆን የዚህ ህግ የፍልስፍና መሰረት ደግሞ መሸጥና መለወጥ ኣይቻልም የሚለው ነው። እንግዲህ መሸጥ ኣይቻልም ሲባል መንግስትም መሸጥ ኣይችልም ባለ መሬቱም መሸጥ ኣይችልም ማለት ነው። በመጀመሪያ ደረጃ ለምንድነው መሬት ከመሸጥና መለወጥ የኢኮኖሚክ ህግ የወጣው? ምን ግዙፍ ጉዳይ ኢትዮጵያ ኣገኛትና ነው መሬት እንዳይሸጥ እንዳይለወጥ ያለችው? ብለን የፍልስፍናውን መሰረት እንድንመረምር ያደርገናል። የመንግስት ሰዎች እንደሚሉት ኣንዱ መሬትን መሸጥ መለወጥ እንዳይኖር የተደረገበት ምክንያት በተለይ በሃገራችን የሚበዛው ገበሬ ድሃ ስለሆነ ትንሽ ሲቸግረው መሬቱን እየሸጠ ይሄድና ሁዋላ ላይ ሄዶ ሄዶ ያንን ጥለነው የመጣነውን የፊውዳሉን ስርዓት መልሰን ቁጭ እንላለን ከሚል ስጋት ነው ይላሉ። ስለዚህም ገበሬውን ለመጠበቅና ሄዶ ሄዶ ሊፈጠር የሚችለውን የመሬት ከበርቴ ስርዓት ለመከላከል መሬት የማይሸጥ የማይለወጥ ሃብት መሆን ኣለበት ይላሉ። በመሰረቱ የፊውዳሉ ስርዓት የሚመለሰው ኣንዳንድ ገበሬዎች ብዙ መሬት እየገዙ የመሬት ሃብታም ስለሚሆኑና ያ የሸጠው ገበሬ የነዚህ የመሬት ሃብታሞች የቀን ሰራተኛ ስለሆነ ኣይደለም። የፊውዳሉ ስርዓት ሊመለስ የሚችልበት እድል የለም። ከሁሉ በላይ ግን ሃብታም እየሆኑ የሚመጡ ገበሬዎች ሌሎች መካከለኛ ወይም ዝቅተኛ ሃብት ያላቸውን ገበሬዎች በእርሻ መሬቶቻቸው ላይ ማሰራት መጀመራቸው የካፒታሊስት ስርዓት መገለጫ ነው። ዋናው መንግስት መጠንቀቅ ያለበት የጉልበት ዋጋን ፍትሃዊነት ማጤንና ሰባዊ መብትን ማስከበር መቻል ነው። ፍትህ ባለበት የካፒታሊስት ስርዓት ውስጥ የሚኖር የሃብት መበላለጥ ላገር ጎጂ ኣይደለም። በፊውዳሉ ስርዓት ጊዜ ፊውዳሉ ጭሰኛውን እንደፈለገ ያደርገዋል። ድሃው የህግ ከለላ የለውም። ፊውዳሉ ከህግም በላይ ነው። ኣሁን ግን የመሬት ከበርቴ ቢፈጠር ይህ ከበርቴ ከህግ በላይ እንዳይሆን መንግስት ኣለ። የሚቀጥራቸውን ሰራተኞች ተገቢ የጉልበት ዋጋ እንዲከፍል ይገደዳል፣ እንዲያከብራቸው ይገደዳል:: በመሆኑም የመሬት ሃብታም ማፍራት ወደ ፊውዳል ስርዓት ኢትዮጵያን ኣይመልስም። ከፍ ሲል እንዳልኩት የህግ የበላይነት ስለሚኖርና መንግስትም ህግን የማስከበር ሃለፊነት ስላለበት ይህ ኣይፈጠርም።

ሌላው በጣም ጉልህ ችግር ደግሞ ኢኮኖሚያዊ ችግሮቹ ናቸው። በኢኮኖሚክስ ውስጥ መግዛትና መሸጥ ዋና ጉዳዮች ናቸው። እነዚህ ከሌሉ ገበያ የለም ማለት ነው። ገበያ ከሌለ ደግሞ እድገትን ማሰብ ኣይቻልም። ፈጠራን ማሰብ ኣይቻልም። መሬት ለሽያጭ ኣይቀርብም ማለት ዲማንድ ኣይታሰብም ማለት ነው። ገበሬው እርሻን የማስፋፋት ፍላጎቱ ይገደባል ኣይታሰብም ማለት ነው። ግብዓቶችን ተጠቅሞ በዚያች ኣንድ ሄክታር መሬት ላይ ካመረተ በሁዋላ ምርቱ ጥሞት ሁለት ሄክታር ባደርገው የበለጠ ምርት ኣገኛለሁ ብሎ እንዳያስብ ተገድቧል ማለት ነው። በገበሬውና በገበሬው መካከል መሸጥና መለወጥ ኣይኖርም ማለት ገበያን ከገበሬው ህይወት ማውጣት ነው። በኣንድ ኢኮኖሚ ውስጥ ዲማንድና ኣቅርቦትን የሚገድብ ህግ ማውጣት ኢኮኖሚ እያዳይንቀሳቀስ ሰንክሎ መያዝ ማለት ኣይደለምን?። የኢትዮጵያ መሬት ከመግዛትና ከመሸጥ ህግ ሲገነጠል በተለይ እንደ ኢትዮጵያ ባለ በእርሻ ላይ በጣም ጥገኛ በሆነ ኣገር ላይ ከፍተኛ የሆነ የማክሮ ኢኮኖሚ ተጽእኖ ያመጣል። ኣንዱ የዚህ ፍልስፍና ግዙፍ ችግር የግብርናውን ኢኮኖሚ የረጋ ውሃ ማድረግ (economic stagnation መፍጠር) ነው። ድንበር ነው እንጂ መሸጥ የሌለበት መሬት በዜጎች መሃል የመሸጥና የመግዛቱ ሂደት መጦፍ ነው ያለበት። መሬት በገበያ ላይ ሲውል ነው ግብርናው የሚያድገው።

ገበሬው የመሸጥና የመግዛት መብቱ ሲነፈግ ኣንዱ የሚያመጣው ሌላ ችግር ገበሬውን “ቢዝነስ ማይንድድ” እንዳይሆን ያደርገዋል። ከብሮች ያርቀዋል። ይህ ደግሞ በሃገር ደረጃ ሲታይ ተጽእኖው በጣም ጉልህ ነው። በግብርናው ኣካባቢ ለሚታየው ሰፊ ችግር ኣንዱ ትልቁ ተጽእኖ ፈጣሪ ጉዳይ ይህ ነው። መሬት የማይሸጥ የማይለወጥ የመሆኑ ጉዳይ ካመጣቸው ቀጥተኛና ተዘዋዋሪ ተጽእኖዎች መካከል ኣንዱ ገበሬውን የንግድ ሰው ኣለማድረጉ ነው። ከዚህም የተነሳ እንደሚታወቀው ኣብዛኛው የዋናዋና ሰብሎች ኣምራች የሆነው ገበሬ በየዓመቱ ምርት የሚያመርተው ለራሱ ነው። ለዓመት ቀለቡ ነው የሚያመርተው። ከራሱ ያለፈ ሰፊ ራእይ እንዳይኖረው ተገድቧል። በዚያች በያዛት በኣማካይ ኣንድ ሄክታር ኣካባቢ መሬት ላይ ትንሽ ባቄላ ለሹሮው፣ ትንሽ ስንዴ ለዳቦው፣ ትንሽ ገብስ ለጠላው ወዘተ ያመርታል። እነዚህን ሲያመርት እያሰበ የሚያመርተው የራሱን የኣመት ቀለብና በልግ ወይ መኸር ሲመጣ የሚያስፈልገውን ዘር ነው። ወደ ከተማ ሄዶ ትንሽ እህሎች የሚሸጠው እንደ ጨው፣ ስኳር፣ ጋዝ የመሳሰሉትን እሱ የማያመርታቸውን ጉዳዮች ለመግዛት ሲያስብ ነው። የከተማው ነዋሪም የሚኖረው በነዚህ ምርቶች ገበሬው እየተነቃቃ በሚሸጠው እህል ነው። ከዛ ውጭ ገበሬው ሁለገብ የእርሻ ስራን ስለሚያካሂድ ኣነሰም በዛም ፍላጎቱን ከጓዳው፣ ከጓሮው ነው የሚያገኘው። ይህም ኣንዱ የገበሬውን የቢዝነስ ሰው ኣለመሆን የሚያሳይ ነው። ገበሬው በመሸጥና በመግዛት ሂደት ውስጥ ኣክቲቭ ሆኖ ኣይታይም። በኣንጻሩ በበለጸጉ ኣገራት የምናየው ደግሞ ገበሬው የሚያመርተው ለራሱ ቀለብ ኣይደለም። ለቢዝነስ ነው። ገበያ እያጠና በሰፊው እያመረተ ያቀርባል። ገንዘብ ባገኘ ቁጥር እየተነቃቃ፣ የተለያዩ የግብርና ግብዓቶችን እየተጠቀመ ምርቱን ከፍ እያደረገ ይነግዳል። ይሄ ነው እድገትን የሚያመጣው። በኢትዮጵያ ውስጥ መሬት የግል ቢሆን ኣንዱ ጥቅሙ ኣንዳንድ ትጉ ገበሬዎች የመሬት ይዞታቸውን ባሰፉ ቁጥር ገበያ ማሰብ ይጀምራሉ። “ቢዝነስ ማይንድድ” ያልነው ጉዳይ ይመጣል። ለመሸጥ፣ ብዙ ብር ለማግኘት ስለሚነቃቁ ምርታቸውን ያሳድጋሉ። የገበያ ዲማንድ እያጠኑ በዚያ ላይ ተመስርተው ምርት ያመርታሉ። ይህ ጉዳይ ደግሞ ምርት እንዲጨምር ከማድረጉም በላይ ገበሬውን ያነቃውና ግብርናው ዘና ብሎ ቢዝነስ ውስጥ ይገባል። እነዚያ ያቺን መሬታቸውን የሸጡ ሰዎች ደግሞ ተጠቃለው ከተማ ይገባሉ ማለት ኣይደለም። ምን ኣልባትም ከኣንድ የእርሻ ስራ ወደ ሌላ የእርሻ ስራ ሊዘዋወሩ ይችላሉ። ኣንድ ገበሬ እርሻውን ትቶ የወተት ላሞች ገዛዝቶ በዘመናዊ መንገድ እያረባ በዚህ ብቻ ለመኖር ሊመርጥ ይችላል። ወይም በኣንዳንድ ሃብታም ገበሬዎች እርሻ ላይ ተቀጥሮ ከዚያ የሚያገኘው የጉልበት ዋጋ ገቢ በዚያች ኣንድ ሄክታር መሬት ላይ ኣርሶ ከሚያገኘው ገቢ ሊበልጥበት ይችላል። ብዙ ምርጫ ይሰጠዋል ማለት ነው። ሌላው ደግሞ ዜጎች በዚህ ዓለም ላይ ኣለኝ የኔ ነው ሊሉት ከሚገባ ሃብት መካከል መሬት ኣንዱ መሆን ኣለበት። በተለይ ገበሬው የባለቤትነት መብቱ ሲነካ በኣለም ላይ ኣለኝ ሊለው የሚገባውን ሊመካበት የሚገባውን የተፈጥሮ ጸጋ መውሰድ ማለት በመሆኑ ትልቅ የመብት ጥያቄ ኣለበት።

በኣሁኑ ጊዜ ከኣዲስ ኣበባ መስፋፋት ጋር ተያይዞ ገበሬዎች ሲፈናቀሉ ኣንዱ የታየው ችግር እነዚህ ገበሬዎች መሬቱ የነሱ ዓይደለምና ሲፈናቀሉ በመሬት ዋጋ መደራደር ኣይችሉም። የተወሰኑ ኣመታት ምርቶቻቸው ተሰልቶ ነው ትንሽ ገንዘብ የሚሰጣቸው። ያ ገንዘብ ደግሞ ቀሪ ህይወታቸውን ኣይለውጥም ብቻ ሳይሆን የተወሰኑ ኣመታት እንኳን ኣይገፋላቸውም። ኣንዱ መሰረታዊ ችግር ይሄ ሆኖ ሳለ በተጨማሪ ከተማዋ ስትስፋፋ እነዚህን ሰዎችም ወደ ሆዷ ማቀፍ ኣለባት። ሰባዊነት በጎደለው መንገድ በኣማካይ ስድስት ቤተሰብ ያለውን ኣንድ ገበሬ ትንሽ ብር ሰጥቶ የሄድክበት ሂድ ማለት በጣም ወንጀል ነው። ከተማዋ ስትስፋፋ የምታቅፈው መሬቱን ብቻ ሳይሆን ህዝቡንም መሆን ኣለበት። የከተማ ነዋሪ ኣድርጋ መዝግባ፣ ቤትና ቦታቸውን ሰጥታ ለቀሪ ህይወታቸው የሚችሉትን ስራ ሰጥታ ከተማዋ ብትስፋፋ ቅሬታ ኣይነሳም ነበር። ዋናው ጉዳይ ግን ከፍ ሲል እንዳልነው በመሬት ባለቤትነት ጉዳይ ላይ ከፍተኛ የፍልስፍና ችግር በመኖሩ ነው ኣሁን በተግባር ችግሮች ኣፍጠው እንዲወጡ ያደረገው። በኣጠቃላይ ግን በግብርናው ኣካባቢ ያለውን ትልቅ ችግር ስናይ በዓለም ታሪክ ረጅም ጊዜ የወሰደው የኢትዮጵያ የመሬት ላራሹ ጥያቄ ላለፉት ሃምሳ ኣመታት ያልተመለሰ ኣሁንም ያልተመለሰ ያደርገዋልና የመሬት ላራሹ ጥያቄ በኣዲስ መልክ ሊነሳ ይገባዋል። በርግጥ መሬት ለኣራሹ ሲባል ለገበሬው ብቻ ሳይሆን ከተሜውም የመሬት ባለቤትነቱን ሊያገኝ ይገባዋል። መንግስት መሬት ኣይሸጥም ይልና ራሱ ግን በሊዝ መልክ የከተማ መሬትን እየቸበቸበ ከፍተኛ ገቢን ያገኛል። ዜጎች ቤታቸውን ሊሸጡ ሲሉ ጣራና ግድግዳው ተተምኖ እንጂ መሬት መሸጥ ኣትችሉም እየተባለ ላልሆነ ህገ ወጥ ስራ ይዳርጋሉ::

ህወሃት መራሹ መንግስት ኣንዱ ከፍተኛ የሆነ ገቢ የሚያገኝበት የሀብቱ ምንጭ የከተማ መሬት ሊዝ ነው። በሌላ በኩል ገበሬው የእርሻ መሬት ባለቤትነት መብቱን ተነጥቆ ሳለ መንግስት ኣገር የሚያክሉ ሰፋፊ ለም የእርሻ መሬቶችን ለመሬት ተቀራማቾች በርካሽ ይሰጣል። በኣንድ በኩል የፊውዳሉ ስርዓት እንዳይፈጠር እሰጋለሁ እያለ ገበሬውን ኣስሮ ይዞ በሌላ በኩል ደግሞ ቤልጂየምን የሚያህል መሬት ለመሬት ቅርምት ተዳርጓል።

ወደ ገበሬው የመሬት ይዞታ ጉዳይ ስንመለስ ህገ-መንግስቱ መሸጥ መለወጥ ይከለክልና መንግስት በሌላ በኩል ማከራየትንና ማውረስን ይፈቅዳል። ማውረስ እየተቻለ ኣይሸጥም። ማከራየት እየተቻለ ኣይለወጥም ይባላል። ገበሬው የሚያርሰውን እርሻ እስከ መቼ እንደሚያስተዳድር የጊዜ ገደብ የለውም። ማውረስም ይችላል። ነገር ግን መሸጥ ኣይችልም። ይህ ኣሰራር ገበሬውን ከገንዘብ ከማራቁ ሌላ በጣም ኣምታች የሆነ ህግ ነው። ግዙፍ የሆነው ሃብታችን እንዲህ ግልጽነት በጎደላቸውና በትክክለኛ የፍልስፍና መሰረት ላይ ባልቆሙ ህጎችና ፖሊሲዎች ላይ ሲመሰረት የሚያመጣው ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ችግር ግዙፍ ነው። በመሆኑም ኣዲሱ ትውልድ ይህን የመሬት ጥያቄ እንደገና ኣንስቶ ሊታገልለት ይገባል። ያሳዝናል የመሬት ላራሹ ጥያቄ ዛሬም በኣምሳ ኣመቱ ኣልተመለሰም። የመሬት ፖሊሲዎቻችን በውነት በጣም በከፋ ችግር ላይ ያሉ ስለሆነ ህዝቡ ከመልካም ኣስተዳደር ጎን ለጎን ኣንድ ዋና የትግል ጥያቄ ኣድርጎ ሊያቀርብ የሚገባው ጉዳይም ነው። የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችም የቀድሞ ወንድሞቻቸው ያነሱትን ይህን የገበሬውን መሰረታዊ ችግር ኣንስተው ሊታገሉለትና የሃምሳ ዓመቱን ትግል በድል ሊቋጩት ይገባል።

እግዚአብሄር ኢትዮጵያን ይባርክ

geletawzeleke@gmail.com

The post መሬት ለአራሹ! appeared first on Zehabesha Amharic.

ግፍ ሲፈጸም ዝምታን ከመረጥን እንደ አገር እንጠፋለን -ሃብታሙ አያሌው |ከቂሊንጦ እሥር ቤት

$
0
0

ለነጻነታቸው በሚያደርጉት ትግል፣ ኢትዮጵያ እንደ እናት ሆና የረዳቻቸዉ ፣ እንደ ጋና፣ ታንዛኒያና ሴኔጋል ያሉ የአፍሪካ አገሮች እንኩዋን ሳይቀሩ የትናየት በደረሱበት ዘመን፣ እንደ ደርግ ዘመን አሁንም በኢትዮጵያ፣ ረሃብና ችጋር የሚገድለን አልበቃ ብሎ፣ ኢትዮጵያዉያን በኢትዮጵያዉያን እጅ እየተገደሉ ነው። 

habtamu ayalew

በቅርቡ በጎንደር እና በኦሮሚያ የተለያዩ ቦታዎቸ እንዳየነው፣ በዜጎች ላይ የደረሰው ግድያ፣ ድብደባና ግፍ እጅግ በጣም ልቤን እንዳደማው መግለጽ እወዳለሁ። ለሞቶት ነፍስ ይማር፣ ለቤተሰቦቻቸዉም መጽናናቱን ያብዛላቸው እላለሁ።

በወገኖቻችን ላይ የደረሰን ጭካኔ አጥብቄ እያወገዝኩ ፣ የአገዛዙ ታጣቂዎች ተቃዉሞ ከሚሰማባቸው ቦታዎች በአስቸኩዋይ እንዲወጡ እጠይቃለህ። መንግስት ገዳዮችን፣ ትእዛዝ የሰጡትን ለፍርድ እንዲያቀርብና ጉዳት ለደረሰባቸው አስፈላጊውን ካሳ እንዲሰጥ እጠይቃለሁ። ገዢዎች የሕዝብን መሰረታዊ ጥያቄ በማናናቅ፣ በሚቆጣጠሩት ሜዲያ በሕዝብ ላይ የሚያሰሙት ዛቻ፣ ማስፈራራት ፣ ስድብ አቁመው፣ ለሕዝብ መሰረታዊ የመብት፣ የነጻነት የፍትህና የመሬት ባለቤትነት ጥያቄዎች አፋጣኝ ምላሽ እንዲሰጡ እጠይቃለሁ።

እኔን ጨመሮ በርካታ ዜጎች በሰላም ሐሳባችንን በመግለጻችን ሽብርተኞች ተብለን፣ ፍትህ ተነፍገን በግፍ ታስረናል። ነጻ ጋዜጦች ተዘግተዋል። በሌሎች አገሮች የእንስሳት መብቶች ሲከበሩ፣ በኛ አገር ግን ለሰብእና ክብር አይሰጥም። ዜጎች በአገራቸው ፈርተዉና ተሸማቀው ነው የሚኖሩት። ብዙዎች ተስፋ ቆርጠው ስደትን መርጠዋል። በልማት ስም ጥቂቶችን ለመጥቀም፣ ገበሬዎች ከእርሻቸው ይፈናቀላሉ። “ከዚህ ብሄረሰብ ናችሁ፣ የናንተ መሬት አይደለም” ተብለው ብዙዎች የዘር ማጽዳት ወንጀል ይፈጸምባቸዋል። በጎንደር ለምለም የአገራችን መሬት፣ ሕዝብ ፓርላማው ሳያውቀው ሊሰጥ እንደሆነ እየሰማን ነው። አገር በ 11% አድጋለች እየተባለ፣ አሥር ሚሊዮኖች ለረሃብ ተጋልጠዋል። ይሄ ሁሉ መቆምና መስተካከል አለበት። “ኢሕአዴግ ልብ ይበል ፤ የጥፋት እጆቹን ይሰብሰብ ፣ ሕዝብን ያክብር፣መሰረታዊ የፖለቲካ ሪፎርም ያድርግ፣ ለብሄራዊ መግባባት ራሱን ያዘጋጅ” እላለሁ።

ነጻነትን ለተጠሙ፣ ፍትህን ለተራቡ ኢትዮጵያዊያን መልእክት አለኝ። ነጻነት፣ ፍትህ ከሌሎች በስጦታ የሚሰጠን አይደለም። ነጻነትና ፍትህ እኛው ራሳችን ታግለን የምናገኘው ነው። በመሆኑም የአገሪቱዋ ሕገ መንግስት እና አለም አቀፍ ሕጎች በሚፈቅዱት መሰረት፣ ሰላማዊ በሆነ መንገድ ድምጻችንን እንድናሰማና ትግሉን እንድንቀላቀል ጥሪ አቀርባለሁ። ግፍ ሲፈጸም ዝምታን ከመረጥን እንደ አገር እንጠፋለን። የአንዱ ሕመም እኛንም ሊያመን ይገባል። እንተባበር፣ እንደራጅ፣ በጋራ፣ በማያዳግም ሁኔታ፣ “በኢትዮጵያችን ከዚህ በሁዋላ በግፍ ደም መፈሰስ የለበትም” እንበል። አሁንስ በቃን !!!!

The post ግፍ ሲፈጸም ዝምታን ከመረጥን እንደ አገር እንጠፋለን -ሃብታሙ አያሌው | ከቂሊንጦ እሥር ቤት appeared first on Zehabesha Amharic.


በተለያዩ ያገራችን ክፍሎች እየተካሄዱ የሚገኙትን ህዝባዊ እምቢተኝነት እነዳይዳፈኑ

$
0
0

አገርና ህዝብ የመበታተን አደጋ ላይ እንዳይወድቅ በጋራ የመቆምና የመታደግ ከፍተኛ አገራዊና ታሪካዊ ኃላፊነት አለብን ታሪካዊ ኃላፊነት አለብን

entc-and-eynm-logoታህሳስ 13፣ 2007 ኢትዮጵያና ህዝቧ ላለፉት 24 ዓመታት ያለ ህዝብ ፈቃድ እያስተዳደረ ባለው በዘረኛው አፓርታይዱ የወያኔ አንባገነን ስርዓት የመልካም አስተዳደር እጦት፣ የፖሊሲ ችግርና እኩይ ተግባር የተነሳ ትልቅ አዘቅት ውስጥ እንድትገባ አድርጓታል። ተፈጥሮያዊ መብት የሆኑት ሰብዓዊና ዲሞክራሲያዊ መብቶችን ነፍጎ ፍፁም አንባገነን በመሆን የህዝባችንን የመኖር ተስፋን በማጨለም ወገናችን መፈጠሩን እስኪጠላ ድረስ የስርዓቱ የክፋት ዱላ ሰላባ ሆኗል። የኢትዮጵያ ህዝብ ነቅቶ በመቆሙ ወያኔ ባይሳካለትም የዘር ፖለቲካን በማራመድ ለዘመናት የቆየውን ኢትዮጵያዊነት ለማጥፋት በሰፊው ሲንቀሳቀስ ቆይቷል። የኢትዮጵያን ህዝብ ለመከፋፈልና ሰልጣኑን ለማራዘም ቋንቋን መሰረት ያደረገው የውሸት ፌዴራሊዝምና አንድ ለአምስት በማቀናጀት በኢሕአደግ ውስጥ በአባልነት አሰባስቦ ሲመራው የነበረ መዋቅር በተገላቢጦሽ የወያኔን አገዛዝ ትልቅ ፈተና ውስጥ እንዲገባ ያደረገበት ታሪካዊ ወቀት ላይም ደርሰናል። ====[ሙሉውን መግለጫ ለማንበብ እዚህ ይጫኑ]—

The post በተለያዩ ያገራችን ክፍሎች እየተካሄዱ የሚገኙትን ህዝባዊ እምቢተኝነት እነዳይዳፈኑ appeared first on Zehabesha Amharic.

ለሱዳን ሊሰጥ ነው ስለተባለው መሬት (ምክር-ለበስ አስተያየየት) –ፍቅሬ ቶሎሳ ጅግሳ

$
0
0

ፍቅሬ ቶሎሳ ጅግሳ፥ፒ ኤች ዲ፥ (የሁማኒቲስ ፕሮፌሰር)

(ፍቅሬ ቶሎሳ፥ ፒ ኤች ዲ – የሁማኒቲስ ፕሮፌሰር)

(ፍቅሬ ቶሎሳ፥ ፒ ኤች ዲ – የሁማኒቲስ ፕሮፌሰር)

መንግሥት ለሱዳን ሊሰጣቸው ነው የተባሉት አሁን በጎንደር አና በቤንሻንጉል አካባቢ የሜገኙት የእነ ኦሜድላና ጋምቤላ መሬቶች በአውነት የማን ናቸው? ያለጥርጥር የኢትዮጵያ ናቸው። ለምን እንደዚህ እንዳልኩ ዝቅ ብዬ አስረዳለሁ። መሬቶቹ በታሪክ የሱዳን ነበሩና ለሱዳን ይሰጡ የሚሉት የኢትዮጵያ ባለስልጣናት መሬቶቹን ለሱዳን ለመስጠት የሚያቀርቡት ምክንያት “በ በሱዳን የእንግሊዝ ቅኝ ግዛት ጊዜ የእንግሊዝ መንግሥት ተወካይ የሆነ አንድ ሻለቃ የወሰን ምልክቱን የተከለው እዛ አካባቢ ነው፤ቀድሞ አፄ ምንይልክ በዚህ ተስማምተው፥ በሁዋላ ደግሞ አፄ ኅይለሥላሴ እና ደርግም ይህን አፅድቀውታል፤” የሚል ነው። በሌላ አነጋገር፥ በታሪካዊ ምክንያት ነው። እዚህ ላይ አንድ አስቂኝ ታሪክ ታወሰኝ። አንድ እንግሊዛዊ ከሱዳን የኢትዮጵያን ድንበር —-

[ሙሉውን ለማንበብ እዚህ ይጫኑ]—

 

 

The post ለሱዳን ሊሰጥ ነው ስለተባለው መሬት (ምክር-ለበስ አስተያየየት) – ፍቅሬ ቶሎሳ ጅግሳ appeared first on Zehabesha Amharic.

ኢሳት ቴሌቪዥን፣ OMN ቴሌቪዥን፣ የአሜሪካ ራድዮ ድምጽ፣  ዘሐበሻ ድረ ገጽ፤ በወያኔ መንግስት በቢሊዮን  ዶላር ወጪ በማድረግ በኢትዮጵያ እንዳይታዩ  ከፍተኛ የሆነ አፈና እየተደረገባቸው ነው። –ከተማ ዋቅጅራ

$
0
0

media

ፌድራል ፖሊስ እንደ ሸለምጥማት ጣራ ለጣራ በመንጠላጠል ዲሽ ሲነቅል ማየታችን ስርአቱ ከፍተኛ ስጋት ውስጥ እንዳለ የሚያሳይ ነው። ዛሬ ዲሻችንን እንደነቀላችሁ ነገ እናንተ ትነቀላላችሁ ዛሬ መብታችንን እንደረገጣችሁ ነገ የእናንተ  እጣ የከፋ እንደሚሆን አትዘንጉ።

አፈናን ዋና አላማው አድርጎ  እየተንቀሳቀሰ ያለው ወያኔ በአገር ቤት ሆነ በመላው አለም በከፍተኛ ሁኔታ አድማጭ እና ተከታዮችን እያፈሩ ያሉትን ነጻ የህዝብ ሚዲያ  አካሎችን የአገሪቱ ንብረት እየዘረፈ በቢሊዮንስ ዶላይ በማውጣት ወንጀል ከመስራት አልፎ ህዝቡ እውነተኛ መረጃን እንዳያገኝ የማፈን ስራዎችን በመስራት ለይ ይገኛል። ወያኔ የሞት ሽረት ትግል በማድረግ ያላቸውን አቅም ሁሉ ለአፈናቸው ተግባር በማሰማራት በኢትዮጵያ ውስጥ ነጻ የሚዲያ አውታሮች እንዳይሰራጭ ከፍተኛ መፍጨርጨር እያደረጉ ነው። የኢትዮጵያ ህዝብ ደግሞ  መስማት የሚፈልገው እውነትን ስለሆነ ዛሬ በይፋ ለማፈን የሚንቀሳቀሱባቸው የሚዲያ አውታሮችን ሁሉም የኢትዮጵያ ህዝብ በሚባል መልኩ የነጻ ሚዲያ አድማጭ ሆኗል። ህዝቡም  እውነተኛ መረጃዎችን የሚያገኝባቸው በዋነኛነት ኢሳት፣ OMN፣ የአሜሪካ ራዲዮ፣ የጀርመን ራሪዮ፣ ዘ-ሐበሻ፣ ECADF፣ ሳተናው፣ Gadaa.com፤ ከመሳሰሉት የህዝብ ሚዲያዎች ሲሆን ከነዚህ ነጻና  ትክክለኛ ዘገባዎችን በመዘገባቸው የተነሳ ለህዝቡ ከፍተኛ ግንዛቤ በመስጠት ላይ ይገኛሉ። ኢትዮጵያ ውስጥ ምን እየተሰራ እንዳለ በስልጣን ላይ ያለው አካል በኢትዮጵያ ህዝብ ላይ ምን አይነት ጥፋትና በደል በመቀየስ አደገኛ አካሄድ እየሄደ እንዳለ ለህዝቡ በግልጽ በነዚህ የሚዲያ አውታሮች  ሲለሚነገራቸው ሁሉም ኢትዮጵያዊ የነዚህ ሚዲያዎች ተከታዮች እና አድማጮች ሆነዋል።

ኢሳት ከጅምሩ ጀምሮ በወያኔዎች  አፈናዎች እየተደረገበት በኢትዮጵያ ውስጥ መሰማት የለበትም ብለው ቢንቀሳቀሱም ኢሳት ግን ከፍተኛ ርብርቦሽ በማድረግ ዜናዎችን ወደ ህዝቡ እንዲደርስ እያደረገ ነው። ኢሳት ለኢትዮጵያ  ህዝብ  ሲተረጎም ኢትዮጵያ ሳተላይት ቴሌቪዥን የሚለውን ትርጉም ሲይዝ ለወያኔዎች እና ለሆድ አደር ካድሬዎች ደግሞ እሳት የሚለውን ትርጉም ይሰጠናል።  ምክንያቱም አይስማማቸውም ይፈጃቸዋል በጓራቸው የሰሩትን ደባ በአደባባይ ይበትነዋል በምሲጢር ያወሩትን ተንኮል በህዝብ ፊት ያጋልጣቸዋል የህዝብን ችግር እና ሃሳብ በነጻነት ወደ ህዝብ ያደርሳሉ።  በዚህ አጋጣሚ ለኢሳት ጋዜጠኖች በሙሉ ከፍተኛ ክብር ያለኝ መሆኑን ለመግለጽ እወዳለው።በተለይ ለሲያይ አጌና፣ ለመሳይ መኮንን፣ለፋሲል የኔአለም፣ እንዲሁም ለሌሎቹ ከፍተኛ አድናቆት እና ክብር አለኝ  የእናንተ ክብራችሁ እውነታችሁ፣ ክብራችሁ ኢትዮጵያ አገራችሁ፣ ክብራችሁ ህዝባቹ ነውና በርቱልን እንላለን።

OMN በኤትዮጵያ ውስጥ በከፍተኛ ሁኔታ እየተሰማ ብዙ  ተከታይ እያገኛ ነው። ወደ መጀመሪያው አካባቢ ላይ በወያኔ መንግስት ምንም ተቃውሞ  ያላጋጠመው ነበረ ወደ በኋላ ላይ ግን ኢትዮጵያ ውስጥ መሰማት የለባቸውም ከሚባሉት ነጻ ሚዲያ ውስጥ ተካቷል። ይህ የሆነበት ደግሞ  የOMN ዋና ዳሬክተር የሆነው አቶ ጀዋር መሃመድ የፖለቲካ ስልት የገባው በመሆኑ ወያኔን ለመጣል ወያኔ በዘረጋው መንገድ ሄዶ ሳይሆን በተቃራኒው ሁሉም ኢትዮጵያዊ በጋራ ሲታገል ብቻ ነው በማለቱ ከወያኔዎች ሃሳብ ጋር በመጋጨቱ በወያኔዎች ጥርስ ውስጥ ሊገባ ችሏል። የወያኔን ዛቻ የማይበግረው ጀዋር ለህዝቡ የሚያስብ ብቻ ሳይሆን ፖለቲካውንም አዋቂ ስለሆነ ስልቱን ወደ ጋራ በመለወጥ ወያኔ የሚፈጽመውን ነገር  የኢትዮጵያ ህዝብ ማሸነፊያው መንገድ አንድነት ብቻ እንደሆነ ስለተገነዘበ ሁላችን የጋራ ጠላታችን ወያኔ ነው በአንድነት እንታገል በማለቱ  ወያኔዎች ስለደነገጡ የመከፋፈል ስራ ለመስራት  ውስጥ ውስጡን በመግባት አማራን እና ኦሮሞን የማጣላት ስራን ሊሰሩ ስለሚችሉ ህዝቡ በንቃት እንዲከታተላቸው እና ይሄንንም ድርጊት የሚሰሩትን  ለፍርድ እንዲቀርቡአቸው በማለት  ሁለቱ ህዝቦች በጋራ መስራት አለባቸው ብሎ  በሳልና የኢትዮጵያ ህዝብ በቀላሉ ነጻነቱን ሊያመጣበት የሚችለውን መንገድ በመያዙ ምክንያት በከፍተኛ ሁኔታ በጀዋር ላይ የስም ማጠልሸት ፕሮፓጋንዳ  ቢነዙም ቅሉ አቶ  ጀዋር ግን ለኢትዮጵያ ህዝብ የጋራ ትግል እናድርግ በማለቱ ፖለቲካው ወደ አሸናፊነት እንዴት እንደሚመጣ የተረዳ ሰው ነው።በOMN ላይ የኦሮሞ  ህዝብ እና የአማራ  ህዝብ ብሎም ሁሉም ኢትዮጵያዊ የማይነጣጠሉ መሆናቸው እየተዘገበ  በመሆኑ በኢትዮጵያ  ውስጥ እንዳይታይ ወያኔዎች አፈና አድርገውበታል በዚህ አጋጣሚ ለOMN  ጋዜጠኞች አድናቆቴን ለመግለጽ እፈልጋለው በተለይ አብዲ ፊጤ፣ በፍቃዱ ሞረዳ እና ሌሎችንም ሳላደንቅ አላልፍም።  ፍቃዱ ሞረዳ ከመድረኩየእናንተ ክብራችሁ እውነታችሁ፣ ክብራችሁ ኢትዮጵያ አገራችሁ፣ ክብራችሁ ህዝባቹ ነውና በርቱልን እንላለን።

ዘ-ሐበሻን ድረ ገጽ ወያኖዎች የሚፈሩት እና ብዝም ግዜ ከዌብ ፔጃቸው ላይ ለማጥፋት ሲሯሯጡ የነበሩት የሚቀርበውን እውነተኛ መረጃ እና ዘገባ በመፍራት ነው። ሁሉም ኢትዮጵያዊ በነጻነት የሚስተናገዱበት የኢትዮጵያ አለኛታ እውነተኛ ነጻ የህዝብ ሚዲያ ድረ ገጽ በመሆኑ ነው። ዘ-ሐበሻ  ወያኔዎች ካስታጠቃቸው አጋዚ ጦር በላይ የኢትዮጵያ ህዝብ እውነታነትን በማስታጠቅ ትታወቃለች። ወያኔ ካሰማራቸው አድማ በታኝ የበለጠ ዘ-ሐበሻ  የወያኔዎችን በህዝብ መሃል የቋጠሩትን ተንኮል ቀድማ በመድረስ ትበትናለች በዘሐበሻ ድረ ገጽ ሁሉም ነገር ይስተናገዳል ዜናዎች፣ የተለያዩ የፖለቲካ ውይይቶች፣ የህዝብ ድምጾች፣ የሙሁራን አስታያየቶች፣ ወቅታዊና ጽሁፎች፣ አገራዊ፣ ፐለቲካዊ እና ማህበራዊ ጉዳዮች ይነበባሉ። በዘሐበሻ  ድረ ገጽ ላይ ሁሉም ኢትዮጵያዊ በነጻነት ለሚዲያው በሚመጥን መልኩ የተጻፉ ስነ ጽሁፎችም ሆኑ እውነተኛ መረጃዎች ያለአድሎ ይስተናገዳሉ። ይህ ደግሞ ለወያኔዎች ትልቅ እራስ ምታት ነው።

ኢትዮጵያዊው ውሸት የግሌ የሚሏት ቴሌቭዝን(ETV) የወያኔዎችን የውሸት ወሬ እንዲሰማላቸው ቢፈልጉም ህዝቡ ግን መልሶ መላልሶ  ነግሯቸዋል። ኢቲቪን ማመን ዘግቶ  ነው፣ ኢቲቪ ውሸት አይሰለቸውም፣ ኢቲቪ ሌባ በማለት ህዝቡ ቢነግሯቸውም ህዝቡን በመስማት እና ወደ እውነተኛ መረጃ ወደ ማስተላለፉ ከመምጣት  ይልቅ የበለጠ ውሸትን ይገልጹበት ጀመረ ሌላው ቀርቶ በኢትቪ መስኮት ብቅ ብለው አንድ አንድ ወያኔዎች የምናየውን እና የምናነበውን ብሎም የምናስበውን መርጠውልን እነሱ የሚሉት ብቻ እንድንከውን  ይፈልጋሉ። ሌላው ቀርቶ  ሼርም ላይክም ማለት እንዴሌለብን ይነግሩናል። የኢትዮጵያ ህዝብ ምን ያህል የወያኔ ውሸት ካንገሸገሸው በጣም ቆዩቷል ሁሉም በሚያስብል መልኩ ኢትዮጵያ ውስጥ ከሚተላለፉት ዜናዎች እና ወቅታዊ ፕሮግራሞች የሚገኝ አንዳችም እውነት የለም። የምንሰማቸው እውነተኛ መረጃ እና ከስሜቱ  አልያም በተመስጦ እየተከታተለ ያለው በዘሐበሻ ላይ እና በሌሎች ነጻ ሚዲያዎች በሚወጡት ዜናዎች ነው። ስለዚህ የዘሐበሻ አዘጋጆችን ላደንቃቸው እፈልጋለው ለኢትዮጵያ ህዝብ በማሰብ ለህብረተሰቡ መረጃን በማቅረብ እና የሚፈለገውን ሁሉ በማስተናገድ ኢትዮጵያ ውስጥ ወያኔ የሚያደርሰውን ጭቆና እና አፈና እንዲታወቅ እንዲሁም ታሪካዊ  እና አስተማራዊ ነገሮችን በማቅረብ ለህዝብ ትልቅ ግንዛቤ እያስጨበጣችሁ ስለሆነ እናንተም ላገራችሁ ኢትዮጵያ ማድረግ ያለባችሁን ነገር እያደረጋችሁ ስለሆነ  አድናቆቴን መግለጽ እፈልጋለው።

በመጨረሻም ማፈን የማይሰለቻቸው ወያኔ ህዝቡ ስለ መብቱ ሲናገር ማፈን፣ የሃይማኖት ሰዎች ስለ ሃይማኖታቸው መብት ሲናገሩ ማፈን፣ የፖለቲካ ሰዎች ስለ ፖለቲካ ሲናገሩ ማፈን፣ ነጻ ሚዲያዎች በኢትዮጵያ እንዳይታዩ  ማፈን፣ ዲሞክራሲያዊ እንቅስቃሴን ማፈን፣ መብትን ማፈን፣ እንደዚህ ሁሉኑም ነገሮች አፍኖ ምን ያህል ግዜ መቀጠል እንደሚችል አናውቅም ማፈን መልስ አይደለም፣ ማፈን ስልጣንን ማራዘሚያ መንገድ አይደለም፣ ዛሬ ሚዲያዎች ያፈናችሁ ቢመስላችሁ ዛሬ ህዝባ ችንን ያፈናችሁ ቢመስላቹ ዛሬ ነጻነታችንን ያፈናችሁ ቢመስላችሁ ነገ አፋኞቹ ታፍነው ለፍርድ እንደሚቀርቡ አንዳችም ጥርጥር የለኝም። ሁሌም ህዝብ እና እውነት አሸናፊ ናቸው።

 

ከተማ ዋቅጅራ

23.12.2015

Email- waqjirak@yahoo.com

The post ኢሳት ቴሌቪዥን፣ OMN ቴሌቪዥን፣ የአሜሪካ ራድዮ ድምጽ፣  ዘሐበሻ ድረ ገጽ፤ በወያኔ መንግስት በቢሊዮን  ዶላር ወጪ በማድረግ በኢትዮጵያ እንዳይታዩ  ከፍተኛ የሆነ አፈና እየተደረገባቸው ነው። – ከተማ ዋቅጅራ appeared first on Zehabesha Amharic.

ከ “ናስ ማሰር –አፍ ማሰር”   –ይገረም አለሙ

$
0
0


ginbot7-supporters-blame-woyaneጊዜው ድሮ ድሮ ነው፡፡ቦታው ደግሞ ዝናር ወይንም ጀበርና ታጥቆ ብረት/ጠብ -መንጃ ትከሻ ላይ ጣል አድርጎ መሄድ አንድም ለአቅመ ወንድነት መድረስ  ሁለትም በሀብት ከሌላው የተሻሉ ተደርጎ የሚታይበት አካባቢ ነው፡፡  ደረስኩ ደረስኩ ያለ ጎረምሳ በወቅቱ ተወዳጅና ተመራጭ የነበረውን ናስ ማሰር የተባለ ብረት/ጠመንጃ  ይገዛና በሀገር በሰፈሩ አንቱ የተባሉና የተከበሩ ሽምግሌ ጋር በመሄድ አባት እስቲ ይህችን ብረት እዩልኛ ይላቸዋል፡፡ ርሳቸውም እያገላበጡ እያዩ ቀዝቀዝ ባለ ስሜት ጥሩ ናት ሸጋ ብረት ናት ይሉታል፡፡ ከገጽታቸውና ከአነጋገራቸው  ጥሩ  ስሜት አንዳልተሰማቸው የተረዳው ጎረምሳ ምነው አባት ሆሳ ነች እንዴ ወጥ አይደለችም? ሲላቸው አረም ሸጋ የሆነች ወጥ ብረት ነች ይሉታል፡፡ አሁንም አነጋራቸው ስላላማረው  ታዲያ ምነው አነጋገርዎ ቀዝቀዝ ቢላቸው  አዎ ልጄ ከናስ ማሰር አፍ ማሰር ነው የሚበጀው ብየ ነው አሉት ይባላል፡፡

የህይወትም  ሆነ የንብረት ደህንነት የሚጠበቀው በጠመንጃ ሳይሆን እጅ በሚሰራው መልካም ድርጊት ከአንደበት በሚወጡ  የታረሙ ቃላት ነው፡፡ በጠመንጃ እየተማመኑና በጡንቻ እያሰቡ የሚሰሩትና የሚናገሩት ሁሉ ጠላት ስለሚያፈራ፡ የህይወትና የንብረት ደህንነት አይኖርም፡፡ ስነ ምግባር የገራውና በራሱ እንዲፈጸምበት የማይፈልገውን በሌሎች የማይፈጽም፤ ፈሪሀ እግዚአብሄርን የተላበሰና አንደበቱ የታረመ ለህሊናው የሚገዛ ሰው ግን  ወዳጅ እንጂ ጠላት ስለማይኖረው በቀንም ሆነ በለሊት በሜዳም ሆነ በጫካ ብቻውን ቢጓዝ የሚያሰጋው ነገር አይኖርም፡፡

በጠመንጃ መተማመን ሲጀመር የማሰብንና የመወሰንን ስራ ጡንቻ ስለሚረከብ የሚሰራው ሁሉ የእብሪት የሚነገረው ሁሉ ለከት የለሽ ይሆንና ወዳጅ እያነሰ ጠላት እየበዛ ይሄዳል፡፡ ይህ አድራጎት በፖለቲከኞች ሲፈጸም ደግሞ የሚያስከትለው ጦስ  ከድርጊቱ ፈጻሚዎች ይልቅ ሀገርንና ሕዝብን ይሆናል የሚጎዳው፡፡

ደርግን ማሸነፋቸው  የፈጠረባቸው እብሪት ሀያ አራት አመት ሙሉ ሊበርድላቸው ያልቻለው  የወያኔ ባለሥልጣናት የህዝብን አመኔታና ፍቅር ለማግኘት የሚያስችለውን  መንገድ  አያውቁትምና ዛሬም ህዝብን ማሰርና መግደሉን መሰብደብና ማፈናቀሉን ቀጥለውበታ፡፡ የንታቸው ብዛትም ይህን ሁሉ የሚያደርሱበትን ሕዝብ  በለከት የለሽ አንደበታቸው ይሰድቡታል፡፡ ትግሉን የማያውቁት የባሩዱን ሽታ ያልቀመሱት አዳዲሶቹ ወያኔዎች ሳይቀሩ የጌቶቻቸውን  ፈር እየተከተሉ ባልዋሉበት ተግባር ሲፎክሩ ባልተገራ አንደባተቸው ህዝብን ሲሳደቡ ሲዝቱና በህዘብ ሲያላግጡ እየሰማን ነው፡፡

ደርግን በማሸነፋቸው ሀያ አራት አመታት ሊበርድ ላልቻለ እብሪት የተዳረጉት ወያኔዎች የጠመንጃ ትምክህታቸው ህሊናቸውን ዘግቶ ማስተዋል ቢነሳቸው እንጂ በተቃራኒው ደርግ ለምንና እንዴት ሊሸነፍ በቃ ብለው ማሰብ ቢችሉና ከናስ ማሰር አፍ ማሰር ብሎ የሚመክር ሽማግሌም በአቅራቢያቸው ቢኖር  ኖሮ በሀያ አራት አመታት ቆይታቸው ከጠመንጃ ትምክህት የህዝብን ፍቅር ወደ ማግኘት ሽግግር ባደረጉ ነበር፡፡

በጠመንጃ አምላኪነት የታበዩት ወያኔዎች በዘመነ ስልጣናቸው ከማናቸውም ወገን ለሚቀርቡ ማናቸውም ጥያቄዎች  የሀይል ርምጃን ዘለፋ ስድብና ፍረጃን ምላሽ አድርገው ኖረዋል ፡፡ በውይይት ሊፈቱ ለሚችሉ ጥያቄዎች  ተቃውሞዎችን ተከትሎ በሚያሰሙት  የለሽ  የለሽ የንቀት ንግግራቸው የበለጠ  ህዝብን እያስቆጡ፣  ህዝቡ ቁጣውን በሰላማዊ ሰልፍ ሲገልጽ ለግድያ ያሰለጠኑትንና ሰዋዊ ባህርይውን አውልቀው የአውሬ ባህርይ ያለበሱትን  ሰራዊት  በማዝመት ያስደበድባሉ፣ ያስገድላሉ ያሳስራሉ፡፡  ሰሞኑን ኦሮምያ ውስጥ የተፈጸመውም  ይሄው  ከጠመንጃ አምላኪነት የተወለደው  አረመኔያዊ ድርጊት ነው፡፡

ከአዲስ አበባ አልፎ አጎራባች የኦሮምያ ከተሞች መሬት አልበቃ ያላቸው ወያኔዎች ገደብ የለሽ የመሬት ፍላጎታቸውን  ለማርካት የዋጡት ነው በሚል ከሁለት አመት በፊት  የአዲስ አበባን ማስተር ፕላንን የተቃውሙ  ዜጎችን በማሰር በመደብደብና በመግደል ተቃውሞውን ለማስቆም የቻለው ወያኔ ሁለት አመት አድፍጦ ከቆየ በኋላ አቶ አባይ ጸሀየ በአደባባይ ወጥተው ማስተር ፕላኑን ተግባራዊ እንደርገዋለን፤ እንቅፋት ለመፍጠር የሚያስብ ካለም ልክ እናስገባዋለን በማለት ለህዝብ ያላቸውን ንቀት አሳዩ ወያኔ ያቀደውን አይደለም ያሰበውን ተግባራዊ ከማድረግ ወደ ኃላ እንደማይልም አረጋገጡ፡፡

አቶ አባይ ጸሀዬ እንዲህ በእብሪትና በድፍረት ለመናገር  የበቁበትን ምክንያት መገመት ይቻላል፡፡ የመጀመሪያው ጠመንጃ የወለደው ማንአለብኝነትና የህዝብ ንቀት ነው፡፡ ሌላው ደግሞ ኦህዴድን ጠፍጥፈው የሰሩት ወያኔዎች፤ መሪዎቹንም ከየምርኮ ሰፈር ሰብስበው ከምርኮኝነት ወደ ድርጅት መሪነት ያሸጋገሩዋቸው እነርሱ በመሆናቸው  ለመቃወም ሞራልም አቅምም እንደሌላቸው ማወቃቸው ነው፡ ለሀያ አራት አመታትም  ወያኔ በኦሮምያ ምድር ያሻውን ሲፈጽም ኦህዴድ የተሰጠውን ተልእኮ ከማስፈጸምና ሰጥ ለጥ ብሎ ከመታዘዝ ውጪ  ትንፍሽ ያለው ነገር አለመኖሩም ለአባይ ጸሀዬ የእብሪት ዛቻና ድንፋታ አስተዋጽኦ አለው፡

ወያኔዎች ያልተረዱት ከባህሪያቸውም አንጻር ሊረዱት የማይችሉት ትናንት ወታደራዊ ምርኮኛ ዛሬ ደግሞ የስኳር ምርኮኛ ከሆኑትና  ወዶ ገብ ሆነው ለወያኔ እጅ ከሰጡት  የኦህዴድ አመራሮች ውጪ  የሆኑ የኦህዴድ አመራሮች መኖራቸውን ፤እንዲሁም የኦህዴድን አመራሮች በምርኮ መያዝ ሕዝብን መያዝ አለመሆኑን ነው፡፡ይህን ደግሞ በአጭር ግዜ በመላ ኦሮምያ የተነሳው ተቃውሞ መማር ለሚችል በበቂ ያሳየ ነው፡፡

የአቶ አባይ ጸሀዬ ድንፋታ በተቃውሞ የቆመው ማስተር ፕላን ተግባራዊ ሊደረግ  መሆኑን በማጋለጡ  ምእራብ ሸዋ ላይ የተነሳው የደን መሸጥን ሰበብ ያደረገው የተማሪዎች ተቃውሞ ምክንያት  ሆኖት ተዳፍኖ የቆየው ተቃውሞ ሲቀሰቀስ በኦህዴድ እና በወያኔ ሰፈር  የተሰሙት ነገሮች መለያየት ምርኮኛም ቢሆን ጫናው ሲበዛበት አሻፈረኝ ሊል፤ሎሌም ቢሆን ንቀቱ ሲብስበት ሊያምጽ እንኳን ባይችል ሊያኮርፍ እንደሚችል ያሳየ ነው፡፡ ውሻ እንኳን በደል ከበዛበት ባይናከስ እንኳን ባለቤቱ ላይ ያጉረመርማል፡፡

ተቃውሞው ዳር እስከዳር ተቀጣጥሎ ኦህዴድን ከነመኖሩም የረሳው ወያኔ ገዳዮችን አሰማርቶ ተማሪዎችን በመግደል ተቃውሞውን አባባሰው፡፡  በቅርቡ የመንግሥት የህዝብ ግንኙነት ምኒስትር የሆነውና  ከማን አንሼ በማለት በስድብና በዛቻ ከዋናዎቹ ወያኔዎች ጌቶቹ ጋር እየተፎካከረ ያለው ግልገሉ ወያኔ  አቶ ጌታቸው ረዳ ደግሞ ሕዝቡን አጋንንት ሰይጣን ጠንቋይ እያለ በመሳደብ እሱም በአቅሙ የወያንን እብሪትና ንቀት በማሳየት በእሳት ላይ ቤኒዚን ጨመረ፡፡ ይህም ኦህዴድ ውስጥ ያሉትን ምርኮኞች፤ ወደ ገቦችና ነጻ ሰዎችን በአንድነት ከሕዝቡ እኩል አስቆጣ፡፡

ሰው የሚናገረው ያደገበትን፣ የተማረውን፣ የኖረበትን ወይም እየኖረበት ያለውን ወዘተ ነው፡፡ በመሆኑም አቶ ጌታቸው በስም ከጠራቸው ነገሮች ጋር ትውውቅ የጀመረው መቼ የትና እንዴት አንደሆነና ስለ እነርሱ እንዲህ በጥልቀት ያወቀበትን ምክንያት ባናውቅም የቅርብ ግንኙነት ያለው መሆኑንን ግን ንግግሩ አሰረድቶናል፡፡ በርግጥም ሲናገር የሚጠቀማቸውን ቃላቶች ብቻ ሳይሆን የፊቱን ገጽታ ጭምር ላስተዋለ ከጠቀሳቸው ነገሮች ጋ የቅርብ ትውውቅ እንዳለው ያስታውቃል፡፡  ባይሆንማ ኖሮ የቱንም ያህል መታበይ  ልቡን ቢደፍነው፣  የቱንም ያህል ጠመንጃ አምላኪነት ማስተዋልን ነስቶ በጡንቻው አንዲያስብ ቢያደርገው፣  የቱንም ያህል ለከት የለሽነት ቢጠናወተው ህዝብን አጋንንት ሰይጣን ብሎ አይሰደብም በጠንቋይነትም አይፈረጅም ነበር፡፡

እብሪት፣ የህዝብ ንቀት፣ ለከት የለሽነት ወዘተ የወያኔ ባህርይ በመሆናቸው አቶ አባይ ጸሀዬ በዛቻና ድንፋታቸው፣ አቶ ጌታቸው ረዳ በለከት የለሽ አንደበቱ በህውኃትዘንድ ሊመሰገኑና ሊወደሱ  እንጂ ሊነቀፉ፣ ሊወገዙና ሊከሰሱ እንደማይችሉ ይታወቃል፡፡ነገር ግን ዘላለማዊ ምድራዊ ኃይል የለምና ጸሀይዋ መጥልቅ የጀመረች እለት ምላሴ ጠንቅ አተረፍሽ ለነፍሴ ማለታቸው አይቀሬ ነው፡፡

ተፈጥሮን ተመክሮ አይመልሰውምና ዋናዎቹ ወያኔዎች የተጠናወታቸው  የህዝብ ንቀት እብሪትና ለከት የለሽነት(አፍ እንዳመጣ መናገር) መግደል መደብደብና ማሰር በውስጣቸው ስር ሰዶ የተዋሀዳቸውና ከዚህ ውጪ ሌላም ስለማያውቁ ይቅርብችሁ በሚል የሚሰጣቸውን ምክር መስሚያ የላቸውም፡፡ ሌሎቹ (መለስተኛና አዳዲሶቹ) እኛም እንደ ጌቶቻችን የሚሉ ካልሆኑ ሌላው ሌላው ቢቀር ከላይ የገለጽናቸው ሽማግሌ ለጎረምሳው እንደመከሩት ከናስ ማሰር አፍ ማሰር ይበጃል ልንላቸው እንወዳለን፡፡

ለኦህዴዶች ደግሞ የመጨረሻው መጨረሻ ሲመጣ ከሁለት ያጣ እንደምትሆኑ አስባችሁት ታውቃላችሁ፡፡ወያኔዎች እስከቻሉና የእናንተ አገልጋይነት እስከቀጠለ ድረስ መላዋን ኢትዮጵያን ለመግዛት፣ ጀንበሯ ማዘቅዘቅ ስትጀምርና በአገዛዛቸው መቀጠል የማይችሉበት ደረጃ ላይ መድረሳቸውን ሲረዱ የሚገቡበት ምሽግ እንዳያጡ  ሁለቱንም ጎን በጎን እየሰሩ ነው፡፡ የትግራይን ሕዝብ ከሌላው ለመነጠል ወገባቸውን ታጥቀው የሚሰሩትና ትግራይን በሁሉም ረገድ ከሌሎች የኢትዮጵ ክፍሎች የበለጠች ለማድረግ የሚጥሩት ለዚሁ ነው፡፡

እናንተ ግን ምን አላችሁ፣ መሬት ከመቀራመትና ፎቅ ከመገንባት ውጪ ምን በጎ ነገር ሰርታችኋል፡፡ እንደውም  ለወያኔ አገላጋይነት አድራችሁ እንወክለዋለን ከምትሉት ህዝብ ጋር ተቆራርጣችኋል፣  ከዚህ አልፋችሁም ደም ተቃብታችኋል፤ የመጨረሻው መጨረሻ ሲመጣ ደግሞ  ወያኔ ሜዳ ላይ ጥሎአችሁ ወደ ምሽጉ ሲገባ ህዝቡ እንዳለየ አይቶ ንቆ የሚተዋችሁ ሳይሆን ለበቀል ይፈልጋችኋል ለፍረድ ያቀርባችኋል፡፡ በዛን ወቅት ወያኔ በምንም እንዴትም ሊታደጋችሁ አይችልም፣ ይልቁንም በአገልጋይነት አድራችሁ በሕዝብ ላይ የሰራችሁትን ሁሉ በማጋለጥ ራሱን ነጣ ለማድረግ ነው ዪዳዳው፡፡ ስለሆነም ወያኔ በጠመንጃ አምላኪነት የሚፈጽመውን የመንግስት ሳይሆን የወራሪ ሀይል ተግባር እናንተ የህውሀት አምላኪ ሆናችሁ ማስፈጸሙን በመቀጠል መጪውን ለመቀበል መዘጋጀት ወይንም በቃን ብላችሁ ከህዝብ የሚያስታርቃችሁን ውሳኔ መወሰን ወቅቱ ዛሬ ነው፡፡ህዝብ እንደሁ ይቅር ባይ መሀሪ ነው፡፡

በዚህ መልኩ አንደ ኦህዴድ አቋም መያዝና ራሳችሁን ነጻ ማውጣት የማይቻል ከሆነ ሁለተኛው አማራጭና ምርጫ ስንዴው ከእንክርዳዱ  ራሱን መለየት ነው፡፡ ከላይ እንደተገለጸው በኦህዴድ ውስጥ የጦርና የስኳር ምርኮኛ፤  ወዶ ገብ ( ለወያኔ ያደሩ)  እና  ነጻ ሰዎች መኖራችሁ ቢታወቅም ራሳችሁን በተግባር መግለጽ እስካልቻላችሁ ድረስ በኦህዴድ ላይ የሚቀርበው ተቃውሞና ክስ በጅምላ ሁላችሁንም ነው የሚመለከታችሁ፡፡ ስለሆነም በአንድ ቅርጫት ገብታችሁ ተንቃችሁ ህዝብን እያስናቃችሁ፤ ተባባሪ ሆናችሁ ህዝብን እያስፈጃችሁ መቀጠልና  የሚመጣውን ለመቀበል መዘጋጀት አለያም በሌሎች ተጠቃሚነትና ጥፋት ተጠያቂ ላለመሆን ሚናችሁን መለየትና የህዝብ ወገን መሆናችሁን በተግባር ማሳየት ፡፡

ምርጫው የእናንተ የመወሰኛ ግዜአችሁም ዛሬ ነው፡፡

The post ከ “ናስ ማሰር – አፍ ማሰር”   – ይገረም አለሙ appeared first on Zehabesha Amharic.

Sport: ያከተመው የበላይነት |የእንግሊዝ ክለቦች በአህጉራዊ ውድድር ተዳክመዋል

$
0
0

 

champions

የእንግሊዝ ክለቦች ከ2004/05 የውድድር ዘመን ጀምሮ በአውሮፓ መድረክ የበላይነቱን ወስደው ቆይተዋል፡፡ ይህ የበላይነት እስከ 2011/12 የውድድር ዘመን ድረስ ዘልቋል፣ በዚህ የስምንት ዓት ጊዜ ውስጥ ማንቸስተር ዩናይትድ፣ ሊቨርፑል እና ቼልሲ የውድድር ዘመኑ አሸናፊዎች ነበሩ፤ አርሰናል ደግሞ የፍፃሜ ተፋላሚ በመሆን የእንግሊዝ ክለቦች ኩራት ነበር፡፡ ከ2003/04 የውድድር ዘመን ጀምሮ እስከ 2011/12 የውድድር ዘመን ድረስ የእንግሊዝ ክለቦች በምድብ ማጣሪያ ሽንፈቱን ያስተናገዱበት ከፍተኛው ቁጥር አምስት ነበር፡፡ በዚህ ዓመት ግን ከወዲሁ (ገና አንድ የምድብ ማጣሪያ የመጨረሻ ጨዋታ እየቀረ) ሰባት ሽንፈቶች ተከስተዋል፡፡ (አራቱ ክለቦች በጋራ ያስመዘገቡት ሽንፈት መጠኑ እጅግ በጣም ከፍ ብሏል፡፡ ውጤቱ በዚህ ቁጥር ወደ ሶስት ዝቅ ሊል ይችላል፡፡ የእንግሊዝ ክለቦች አወራረድ ምን ይመስላል? ተከታዩ ፅሑፍ ምላሽ አለው፡፡

2000/05

የሊቨርፑል ተአምር የታየበት የኢስታንቡሉ የፍፃሜ ጨዋታ የመርሲሳይዱ ክለብ 3ለ0 ከመመራት ተነስቶ ቻ ከተለያየ በኋላ በመጨረሻም በመለያ ምት ያሸፈነበት ነበር፡፡ ‹‹የኢስታንቡሉ ተአምር›› የሚል ስያሜ ያገኘው የፍፃሜ ጨዋታ የእንግሊዝ ክለቦችን አነቃቅቷል፡፡ በግማሽ ፍፃሜው ቼልሲን ያሸነፈው የአሰልጣኝ የራፋ ቤኒቴዝ ቡድን ሻምፒዮን የሆነበት መንገድ ዛሬም ድረስ የመወያያ ርዕስ ሆኗል፤ በዚያ የውድድር ዘመን አርሰናል እና ማንቸስተር ዩናይትድን ያሸነፈው በውድድሩ በሁለተኛው ዙር ነበር፡፡

በሁለተኛው ዙር የቀረቡ የሊጉ ክለቦች ቁጥር፡-4

ሩብ ፍፃሜ የደረሱ የሊጉ ክለቦች ቁጥር፡- 2

2005/06

በስታድ ደ ፍራንስ አርሰናል በባርሴሎና 2ለ1 የተሸነፈበት የፍፃሜ ጨዋታ ፍፁም የሚያስቆጭ ነበር፡፡ የእንግሊዝ ክለቦችን ከሩብ ፍፃሜ ጀምሮ በመወከል ብቸኛ የነበረው የሰሜን ለንደኑ ክለብ ታሪክ ሊሰራበት የተቃረበበት አጋጣሚ መቼም ቢሆን አይረሳም፡፡ ቼልሲ እና ሊቨርፑል ጉዟቸው ከሁለተኛው ዙር ሲገታ ማንቸስተር ዩናይትድ ከምድብ ማጣሪያው ማለፍ አልቻለም፡፡

በሁለተኛው ዙር የቀረቡ የሊጉ ክለቦች ቁጥር፡- 03

ሩብ ፍፃሜ የደረሱ የሊጉ ክለቦች ቁጥር፡- 1

2006/07

ሊቨርፑል በ2004/05 የውድድር ዘመን ለፍፃሜ ከቀረበው ኤሲ ሚላን ጋር በድጋሚ መገናኘቱ ትኩረትን ቢስብም የአቴንሱ የፍፃሜ ጨዋታ በጣልያኑ ክለብ 2ለ1 አሸናፊነት ተጠናቅቋል፡፡ ሆኖም ሊቨርፑል፣ ቼልሲ እና ማንቸስተር ዩናይትድ ለግማሽ ፍፃሜ መድረሳቸው ለፕሪሚየር ሊጉ እንደ በጎ ዜና ሊወሰድ ይችላል፣ አርሰናል በሁለተኛው ዙር በፒ.ኤስ.ቪ አይንድሆቨን በደርሶ መልስ ተሸንፎ ከውድድሩ ውጭ ለመሆን ተገድዷል፡

በሁለተኛው ዙር የቀረቡ የሊጉ ክለቦች፡- 4

2007/08

በሞስኮው ሉዝኒስኪ ስታዲየም ሁለት የእንግሊዝ ክለቦች ለፍፃሜ ቀርበው መደበኛው ሰዓት 1ለ1 ከተጠናቀቀ በኋላ ማንቸስተር ዩናይትድ ቼልሲን በመለያ ምት 6ለ5 አሸንፎ ከ1999 በኋላ የቻምፒዮንስ ሊጉን ዋንጫ ኦነግ፣ በሩብ ፍፃሜው አርሰናልን ያሸነፈው ሊቨርፑል በግማሽ ፍፃሜ ጨዋታ ለቼልሲ እጅ ሰጥቶ ለፍፃሜ ለመግባት ሳይችል ቀርቷል፡፡

በሁለተኛው ዙር የቀረቡ የሊጉ ክለቦች፡- 4

2008/09

ማንቸስተር ዩናይትድ፣ ቼልሲ፣ አርሰናል እና ሊቨርፑል በተሳተፉበት ውድድር ሊቨርፑል ከምድብ ማጣሪያው ሲወድቅ የተቀሩት ሶት ክለቦች ለግማሽ ፍፃሜ ደረሱ፣ ቼልሲ በባርሴሎና ተሸንፎ ለፍፃሜ ለመግባት የነበረው ህልም ሳይሳካ ቀረ፡፡ ማንቸስተር ዩናይትድ አርሰናልን አሸንፎ ለፍፃሜ ቢቀርብም በባርሴሎና ሮም ኦሎምፒክ ላይ 2ለ0 ተረታ፣ ሶስቱ የእንግሊዝ ክለቦች በምድብ ማጣሪያው በጋራ ሽንፈትን ያስተናገዱት በሁለት አጋጣሚዎች ብቻ ነበር፡፡

በሁለተኛው ዙር የቀረቡ የሊጉ ክለቦች፡- 3

ሩብ ፍፃሜ የደረሱ የሊጉ ክለቦች፡- 3

2009/10

ማንቸስተር ዩናይትድ፣ አርሰናል እና ቼልሲ ምድብ ማጣሪያዎችን ሲያልፉ ሊቨርፑል ወደ ቀጣዩ ዙር ማለፍ ተሳነው፡፡ በሁለተኛው ዙር ቼልሲ የውድድሩ አሸናፊ በሆነው ኢንተር ሚላን ሲሸነፍ፣ ማንቸስተር ዩናይትድ እና አርሰናል ከሩብ ፍፃሜ ማለፍ ተሳናቸው፡፡

በሁለተኛው ዙር የቀረቡ የሊጉ ክለቦች፡- 3

ሩብ ፍፃሜ የደረሱ የሊጉ ክለቦች፡- 2

2010/11

ማንቸስተር ዩናይትድ ለፍፃሜ በቀረበበት የውድድር ዘመን በባርሴሎና ዌምብሌይ ላይ 3ለ1 ተሸንፎ ዋንጫ ለማንሳት የነበረው ህልም ሳይሳካ ቀረ፣ አርሰናል በሁለተኛው ዙር በውድድሩ አሸናፊ ባርሴሎና በተረታበት አጋጣሚ ቶተንሃም እና ቼልሲ ሩብ ፍፃሜ ድረስ መጓዝ ችለው ነበር፡፡

በሁለተኛው ዙር የቀረቡ የሊጉ ክለቦች፡- 4

ሩብ ፍፃሜ የደረሱ የሊጉ ክለቦች፡- 3

2011/12

በፕሪሚየር ሊጉ 6ኛ ደረጃን ይዞ የፈፀመው ቼልሲ በቻምፒዮንስ ሊጉ የፍፃሜ ጨዋታ ከባለሜዳውን ባየርን ሙኒክ በመደበኛው ጨዋታ 1ለ1 ተለያይቶ በመለያ ምት አሸንፎ ሻምፒዮን የሆነበት መንገድ በጣም አስገራሚ ነበር፡፡ ማንቸስተር  ዩናይትድ እና ማንቸስተር ሲቲ ከምድብ ማጣሪያው በተሰናበቱበት የውድድር ዘመን የአርሰናል ጉዞ በሩብ ፍፃሜው በመገታቱ ቼልሲ ረጅም ርቀት ተጉዞ ያስመዘገበው ስኬት የእንግሊዝ ኩራት እንዲሆን አስችሎታል፡፡

በሁለተኛው ዙር የቀረቡ የሊጉ ክለቦች ቁጥር፡- 2

ሩብ ፍፃሜውን የተቀላቀሉ የሊጉ ክለቦች ቁጥር፡- 1

2012/13

ቻምፒዮንስ ሊጉ በአዲስ መልክ ከ2003 ጀምሮ ከተዋቀረ በኋላ በሩብ ፍሜው አንድም የእንግሊዝ ክለብ ያልተገኘበት የውድድር ዘመን ነበር፣ ይህ የእንግሊዝ ክለቦች አቅም እየተዳከመ የመምጣት ምልክት አንድ አካል ተደርጎ ይወስዳል፡፡ አርሰናል እና ማንቸስተር ዩናይትድ ከሁለተኛው ዙር የተገታው ጉዟቸው ሩብ ፍፃሜ ለመግባት የነበራቸውን ህልም መና ሲያስቀረው ማንቸስተር ሲቲ እና ቼልሲ ከምድብ ማጣሪያው እንኳን ማለፍ አልቻሉም ነበር፡፡ ሲቲ በምድብ ማጣሪያው አንድም ጨዋታ አለማሸነፉ በብቃቱ ላይ ጥያቄ አስነስታሏል፡፡

በሁለተኛው ዙር የቀረቡ የሊጉ ክለቦች ቁጥር፡- 2

ሩብ ፍፃሜው የተቀባቀሉ የሊጉ ክለቦች ቁጥር፡- 0

2013/14

በሊዝበን ስታድ ደ ሉዝ ሁለቱ የማድሪድ ክለቦች ለፍፃሜ ቀርበው ሪያል ማድሪድ ለ10ኛ ጊዜ ይህንን ዋንጫ ማንሳት ችሏል፣ ባርሴሎና ደግሞ የሩብ ፍፃሜ ተፋላሚ ሆኖ በአትሌቲኮ ማድሪድ ያስተናገደው ሽንፈት ግማሽ ፍፃሜ እንዳይገባ አድርጎታል፡፡

ማንቸስተር ዩናይትድ ማንቸስተር ሲቲ፣ አርሰናል እና ቼልሲ ረጅም ርቀት ለመጓዝ የነበራቸው እቅድ የምዕራ ለንደኑን ክለብ ብቻ ግማሽ ፍፃሜ አድርሶ የቀሪዎቹን ሶስት ክለቦች ጉዞ ከሁለተኛው ዙር በላይ እንዳይጓዝ አድርጓል፡፡

በሁለተኛው ዙር የቀረቡ የሊጉ ክለቦች ቁጥር፡- 4

ሩብ ፍፃሜውን የተቀላቀሉ የሊጉ ክለቦች ቁጥር፡- 1

2014/15

በሶስት ዓመት ጊዜ ውስጥ አንድም የእንግሊዝ ክለብ በሩብ ፍፃሜ ያልተስተዋለበት የውድድር ዘመን ነበር፡፡ አርሰናል፣ ቼልሲ እና ማንቸስተር ሲቲ ወደ ሁለተኛው ዙር ሲገቡ ሊቨርፑል ከምድብ ማጣሪያው እንኳን ማለፍ አልቻለም፡፡ በአንፃሩ ከስፔን ክለቦች ሶስቱ ሩብ ፍፃሜ ደርሰዋል፡፡

በሁለተኛው ዙር የቀረቡ የሊጉ ክለቦች፡- 3

ሩብ ፍፃሜ የገቡ የሊጉ ክለቦች፡- 0

The post Sport: ያከተመው የበላይነት | የእንግሊዝ ክለቦች በአህጉራዊ ውድድር ተዳክመዋል appeared first on Zehabesha Amharic.

አውራ ዶሮ ጮኸ |ከመኳንንት ታዬ

$
0
0

ethiopian Flag

መፈጠር ለመኖር እንደሆነ ስናስበው አንዳችን ከአንዳችን ጋር በአንድም በሌላም መልኩ ተዋህደን መኖራችን ተፈጥሮ በሯሷ ያስተማረችን እውነት ነው።ይሁንና በአብሮነታችን ታሪካችን ፤ባህላችን፤ሐይማኖታችን ወዘተ፤የመሳሰሉት  ሁነቶች የጋራ የሆነ ነገር እየፈጠርን አንደኛው ለሌላኛው በቅብሎሽ እየተዋረሰ እንዲኖር አስችሎት አመቱን እንደ እለት እንዲኖር  ውበት አድረጎ ታጋርቶታል።በዚህ ባህሉ የነገሮችን መፈጠር  በሚመስለው ነገር ሲተረጉም እና የመመራቱ ሄደት ከትውልድ ትውልድ ሲሸጋገር አለ።ለዚህ ነው በርዕሴ ዶሮ ጮኸ ለማለት የወደደኩት;;

ነገሩ እንዲህ ነው። በሐገራችን  አውራ ዶሮ ንጊቱን ለማብሰር  የሚጮህበት  ሰዐት አለው ።የሁሉም እምነት አንድ ነው ።በተለይ እንደ ኢትዮጲያ በብዙ የባህል ድርብርቦሽ የምትኖር ሃገር  ሁሉንም ብሄር ፤ሐይማኖት አንድ ሊያደርግ  የሚችል ብዙ የመሃል ነገር ያላቸው ህዝቦች ከውበታቸው አንዱ እንዲህ ያለው መተሳሰር ነውና ፤ አውራ ዶሮ የሚጮኸው ንጊቱን ለማብሰር  መሆኑን ከዳር አስከዳር  ይስማሙበታል።ይብሰን ብሎ አማርኛው በስነ ቃል ያስረዋል።”ዶሮ ከጮኸ የለም ለሊት ቡሄ ካለፈ የለም ክረምት”። እና ታዲያ አውራ ዶሮ ያለግዜው የጮኸ እንደው “አሁንስ ይህ መንግስት በቃለት አውራ ዶሮ ያለ ግዜው  ጮኸ “ይባላል።ታዲያ በአውራ ዶሮ ጩኸት የትኛው መንግስት እንደወረደ ባላውቅም  ሰሞኑን  የተነሳው ሰደድ እሳት የአውራ ዶሮን ጩኸት እንዳስታውስ  አድርጎኛል።አሁን የምፈራው  መንግስታችን ይህን ሚስጥር ካወቀ አውራ ዶሮች ሁሉ ባሉበት ተይዘው ይታረዱልኝ  ያለ እንደው ነው። ግን ቀኑ ከደረሰ ሴቷም ቢሆን ትጮሃለች ።

 

አውራ ዶሮን  ሁሉ መግደል ጩኸቱን ማሳነስ እንጂ ሊሆን ያለውን መመለስ አይቻልም።ኢትዮጲያዊ ተስፋውን ከእምነቱ ጋር ያዋደደ ብልህ ፍጡር ነው ።ማንነቱ ካመነበት  ፈቀቅ የሚያደርገው ቢመስል የሚደገፍበት የቀን ጀግና ዋስ እስከሚሆነው እንጂ ጨርሶ አንቀላፍቶ አልነበረም።ሁሉን በነገ የተሻለ ቀን እያሰበ ላለመደው ስርዐት በማያውቀው ነገር የሚያውቀው የትላንቱ እየተሰበረና እየጠፋ ቢበዛበት እንኳን ፤ስለሚወዳት ሃገሩና ህዝቡ ፤ስለ ሃይማኖቱና አንድነቱ መታገስን ገንዘብ አድርጎ ከስፍር የፈሰሰ ትግስት  አድርጎ ሲኖር ማየት ከምንም በላይ ነበር።እስቲ አሁን በስልጣን ላይ ያለው መንግስት  በትረ ስልጣኑን ከያዘ እንኳን  ምን ተሰፈረለት።ዘረኝነት፤ርሃብ፤ስደት፤ውርደት፤የማያውቀው ባህል ባለቤት፤የራሱ የሆኑት ሁሉ አሴቶች አራግፎ የምዕራብዊያን ባህልና ውራጅ ናፋቂ እንዲሆን ማድረግ ፤ሃገር እንዳለው ማስረሳትና የጥቂቶች የበላይነት  እያመሰገነ እንዲኖር ማድረግ፤ ሙሰኝነት፤ግብረ ሰዶማዊነት……አረ ስንቱን ።ይህ ሁሉ አነሰና  መንግስት እና ህዝብ አብሮ መኖር ቀረና  ማን እንደሚመራው እንኳን በውል የማያውቀው ህዝብ ከማንትህ አባረንሃል ከቄየህም  እናባርህ ቢሉት ተቆጣ  ።በዛ አለ።ምላሹ ግን ልክ ነህ አልነበረም ።ያው እንደተለመደውና  እንደሚታወቀው ሆነ።እሺ እሱም ይሁን  እግዚአብሔር  የወደደውን አደረገ እንበል ፤ ግንሳ  መንግስት  ያላት  ሀገር  መተዳደር ያለባት  በአግባቡ ሆኖ ሳለ አዘዥና ነዛዡ ሳይታወቅ   በስልጣን ላይ ያሉት ከህዝብ ጋር  ፤ከፓርቲ ጋር ፤ከሐገር ጋር  ሁሌም ጥል ናቸው ።ሁሌም መደባደብ ሁሌ መግደል ሁሌ ማሰር  ብቻ ሁሌ የሆነ ነገር አለ።ይህ ከምን በመነሳት እንደሆነ ግራ ያጋባል ።እውቀት ቢጠፋ  የተፈጥሮ ክህሎትን በመጠቀም  ማስተዳደር ይቻላል። ዘጠና ሁለት ሚሊዮን ሕዝብ  አለ እና  ዘጠና ሁለት ሚሊዮን ሐሳብ ሊኖር ይችላል።

ይህን ሁሉ መንግስት አደለም እራሱ የሐሳቡ ባለቤት  እራሱን ማስተናገድ የማይችልበት ሁኔታ አለ።ግን  መንግስት  የሐገሩ  አሳዳሪ ከሆነ ለራሴ ያለውን  እንኳን  ተጠቅሞ ማስተዳደር  የአባት ነበር።ግዴለም እውቀት ይጥፋ ፤ ጠዋት በቴለቪዥን መስኮት  ወጥቶ በሰላም ያሳደረ በሰላም ያውለን  የኢትዮጲያ ህዝብ ሆይ  በፀሎትህ  አስበን  ከዚህ  ያለፈ እውቀት የለንም ቢባል ፤ የሐገሩ ባህል ነውና ሁሉም  የበኩሉን ለማድረግ  ይሯሯጥ ነበር።ያ እንዳይሆን  እናውቅልሃለን ተባለ ።በምታውቁት ልክ  አሳድሩን  ፤አስተዳድሩን ሲባለ ፤ልጅ አዋቂ   ወንድ ሴት ሳይባል ፤አንድ ሲባል ድብደባ አለፈ ሲባል እስር  ፤ጨመረ ሲባል  ግድያ፤  የእለት ከእለት  ተግባር ሆነና አረፈው።ሁሉን ማድረግ  ይቻል  ይሆናል  ሐሳብን  ግን  አስቀድመን  ከጠቀስናቸው አንዱንም  ማድረግ አይቻልም።የሚቻለው ነገር ቢኖር በጋራ  እኩል ሆኖ አስቦ የእኩል ሐገር ማድረግ ነው።እሱም ብቻ አደለም ፤ መንግስት  እኮ የህዝብ ወላጅ ማለት ነው።ትልቁን እንደ ትልቅ  ትንሹንም እንደ ትንሽ ይዞ ሲያበቃ  አይቶ እንዳላየ ሰምቶ እንዳልሰማ  ሆኖ የሚያልፍ  ሆደ ሰፊ ወላጅ ነው።ይህ ካልሆነ ማነው ባለቤቱ? መቼ ነው እፎይታው? ማነው  እሱ እፎይታ ሰጭው? ሁሉም መልስ የሚያሻቸው ጥያቄዎች ናቸው።

 

የህዝብ ቁጥር ላይ በስልጣን ከመኖር   በየ አንዳንዱ ልብ ውስጥአብሮ መኖር  የብልህነት አንዱ አካል ነው ።ወደ ሕዝብ ሐሳብ  መሄድ እንጅ ሕዝብን ወደራስ  ሐሳብ  መጎትት ትከሻን ከማድከም ያለፈ  ድካም አይዘልም። ብሔራዊ እርቅም  ለመነጋገር መፈለግም  የሚወልዱትን  አውቆ እንደ ማሳደግ ነው ።ይህ ሁሉ ሳይሆን በመቅረቱ  እና የሞኝ አስተዳደር በብልሆች ሃሳብ ማደርም መክረምም አልሆነለትም።ብትናገር ልክ እናስገባሃለን ፤አጋንት ጠንቋይ የሚሉ የመንደረኛ ገፊ ቃላት ባደባባይ መነገር መጀመራቸው የዚሁ የደካማ አመለካከት ፍሬ ሃሳቦች ናቸው።በጦር መሳሪያ ብዛት መታመን በየአንዳንዱ ሰው ልብ  ውስጥ ስንት ጦር እንዳለ አለማወቅ ኋላቀር አመለካከትን ስድስተኛ የስሜት ህዋስ ሆኗአል ማለት ነው።መቼም ልብ ያለው ልብ ይላል።ከዚህ በኋላም  እንደ ትላንቱ የሚታሰብ ከሆነ ህዝቡን ብቻ ሳይሆን የምትጠሉት  ሮጠው የማያመልጡ ውላጆቻችሁንም(የተዋለዷችሁንም) መሆኑን ማመን ይገባል ባይ ነኝ።ለሁሉም መልስ ሊሆን የሚችል ብሔራዊ እርቅ አደርጉና ሁሉንም የሚወክል  ህዝባዊ መንግስት መመስረት ዋነኛና ብቸና አማራጫችሁ መሆኑን የአቅሜን ማስታወስ  እወዳለሁ።በዚህ አጋጣሚ ሳዳምን፡ጋዳፊንም እጣቸውን እናንተም ባታወጡ ምኞቴ ነው ።

 

በጥቅሉ መሰረታዊ በሆኑ ጉዳዮች ላይም ሆነ ባልሆኑ ጉዳዮች ላይ  የህዝብ  የበላይነትን በማክበር  የወጡበትን ማህበረስ ከራስ እኩል አድርጎ ማየት ውሎ አድሮ አክባሪውን  ያከብር  እንደሁ ነው እንጂ አያዋርድም ።ይህ በታሳቢነት ቢያዝ  ከመጥን በላይ   ከመተኛትም ሆነ እንቅልፍን ሳይጠግቡ ከመንቃት  ያድናል።ሁለቱም የጤና አደሉምና።

ቸር እንሰንብት !

The post አውራ ዶሮ ጮኸ | ከመኳንንት ታዬ appeared first on Zehabesha Amharic.

አዲስ አበባ … “አዲስም” – “አበባም” የማያደርጓት 12 ነገሮች

$
0
0

addis ababa

ከደምስ ሰይፉ

1) (የመኪና ጋጠ ወጥ ጥሩንባ) …

በተለይ ሃይገር፣ ሲኖ ትራክና ቅጥቅጥ አይሱዙ … ክላክስ መንገደኛን ማስጠንቀቂያና ከፊት ያለን መኪና ማንቂያ የመሆኑ ፋሽን ድሮ ቀረ… ምንም በሌለበት ሁሉም እየተነሳ ያንባርቅብሃል… ሰፈር ውስጥ ነኝ፣ ት/ቤት ሊኖር ይችላል፣ የሕክምና ማዕከል በአቅራቢያዬ አለ፣ እንስሳ ላስደነብር እችላለሁ… ወዘተ የፍንዳታ ሹፌሮች አዕምሮ ላይ በስህተት የማይከሰት ቁምነገር ነው… መንገድ ተዘጋግቶባቸው ተሰልፈው በቆሙና ወዴትም ሊሄዱ እንደማይችሉ በሚታወቅ መኪኖች ላይ የጥሩንባ እሩምታ መልቀቅ ምን ይባላል?…

addis ababa

2) (ንጽሕና) …

ሰፈር ለይታ ያጸዳችውን ሰፈር ለይታ ታከማቸዋለች… አንዱ መንደር የቆሻሻ ጥዩፍ፣ ሌላው ቀዬ የቆሻሻ እቅፍ ነው የሚመስለው… ሰውም የንጽሕና ጉዳይ ጉዳዩ አይደለም… ታክሲ ውስጥ የጫማ ሽታ ይሰነፍጥሃል፣ መንገድ ላይ የመጸዳጃ ቅርናት ያፍንሃል… ሁሉም የየቤቱን ጉድ በየጥጋጥጉ መድፋት አይጎረብጠውም… በጠራራ ጸሐይ አጥርና የቆመ መኪና ተጠግቶ ሲያንፎለፉለው የማያፍር እልፍ ነው…

3) (ጩኸት) …

ያረጁ ተሽከርካሪዎች ድምጽ የነዋሪው የኑረት ሳውንድ ትራክ ነው… ከአገልግሎት ሰጪዎች የሚለቀቁ ድምጾች ጸጥታን በሲዲ የሚሸጥ አሳታሚን ያስመኛሉ… የሚያንገሸግሽህን ዘፈን ራስ ምታት ከሚለቅ ድምጽ ጋር ትሰማለህ… ዝግ ብለው ስክነት የሚቸሩህን ዜማዎች የምትሰማው ባለታክሲውና ባሬስታው ዝግ ያሉ ሲሆኑ ነው… ሙዚቃው ይፈጥናል… መኪናው ይፈጥናል… አደጋውን አስበው… የትም ሂድ ማጫወቻውን የያዘው ሰው የሚመርጥልህን ጩኸት እንጂ አንተ የምትሻውን ጸጥታ ማጣጣም ዘበት ነው… ነዋሪው ቲአትር እያየ ያወራል፣ እየበላ ያወራል፣ አብሮህ ቁጭ ያለ ሰው ካንተ ጀርባ እርቆ ከተቀመጠ ሌላ ሰው ጋር የሚነጋገር ይመስል እየጮኸ ያወራል… እሪ ብሎ የሚጮህ የስልክ ጥሪ አሰምቶህ እሪ ብሎ እየጮኸ ስልክ ያናግራል… የሐይማኖት ተቋማት ከግቢው ምዕመን በሚተርፈው ድምፃቸው ሰላም ይነሱሃል…

Public transport, Addis Ababa, Ethiopia, Africa

4) (ችኮላ) …

ለመዝናናት የወጡ ጥንዶች ሳይቀር ይቸኩላሉ፣ ታክሲው ይቸኩላል፣ መንገደኛው ይቸኩላል… ለአንድ እንግዳ ሰው ‘ዝናብ መጣ እንዴ?’ የሚያስብል ችኮላ… በችኮላ ይወራል፣ በችኮላ ይበላል፣ በችኮላ ይሰራል፣ በችኮላ ይፈርሳል፣ በችኮላ ቃል ይገባል፣ በችኮላ ቃል ይበላል…

5) (በረሃማነት) …

ጸሐይ መታኝ ልጠለል ብትል ዛፍ የሚባል ታሪክ የለም… አረፍ ብዬ ልተንፍስ ብትል መቀመጫውም መተንፈሻውም የለም… ከፍለህ የምትቀመጥበት እንጂ ደክሞህ የምታርፍበት አንዲትም ታዛ የለችም…

6) (ግለኝነት) …

እንኳንና የሩቅ ሰው ቤተሰብም እርስ በርስ አይፈላለግም፣ ጉርብትና የቤቶች መቀራረብ ስያሜ እንጂ የሰዎች መተሳሰብ መጠሪያነቱ አክትሟል… እንኳን ፊትህን አይቶ ማዘን ችግርህን ነግረኸው መረዳዳት ቀርቷል…

ethiopia 3

7) (ስግብግብነት) …

ባለሃብቱ በሰበሰበው አይረካም… መካከለኛው ባለው አይደሰትም… ያለው ለሌለው አያዝንም… አከራይ በየሩብ ዓመቱ ኪራይ ይቆልልብሃል፣ ነጋዴው በብዙ እጥፍ ያተርፍብሃል፣ ሬስቶራንቶች የሚያቀርቡልህን ምግብ መጠን በመቀነስና የሚጠይቁህን ዋጋ በመጨመር የሚስተካከላቸው የለም… ነግ በኔ ተረት ነው፣ ለሕሊና መኖር ወሬ ነው…

8) (ዘረፋ) …

በጠራራ ጸሐይ ጉንጭህን ለቡጢ፣ ጎንህን ለሴንጢ የሚዳርጉ እልፍ ናቸው… ሞባይልና ላፕቶፕ ይዘህ ማን አለብኝ ብሎ መጓዝ – ‘ባክህ ናልኝ መዘዝ’ የማለት ያህል ነው… የሕዝብ የምትለው ተቋም ውስጥ ‘በእጅህ ካልሄድክ’ ጉዳይህ ዳር አይደርስም… ብዙ ካላስጨበጥክ ጥቂት አታገኝም… አስተናጋጅ ባንተ ሳንቲም ለራሱ ቲፕ ይቆርጣል… ረታክሲ ዳት መልስ ስትጠይቀው ይገላመጣል… ሱሰኛው ልክ ወስኖ ብር ይጠይቅሃል…

drink

 

9) (መሸተኝነት) …

ከልጅ እስከ አዋቂ የቢራ አንገት ጨባጭ ነው… መዝናኛው ቢራ ነው፣ መተከዣው ቢራ ነው፣ ግብዣ – ድግስና መሰባሰቦች ሁሉ ቢራ ናቸው… ታክሲ ውስጥ ሬዲዮው ‘ጠጣ’ ይልሃል፣ እቤትህ ቲቪው ‘ጠጣ’ ይልሃል፣ መ/ቤትህ ጋዜጣው ‘ጠጣ’ ይልሃል፣ መዝናኛ ቦታህ ወዳጅህ ‘ጠጣ’ ይልሃል… መንገዱ ሁሉ ‘ጠጣ’ ‘ጠጣ’ ‘ጠጣ’ ብሎ እንዳዛጋ ነው…

10) (እምነት ማጉደል) …

ብዙ ባሎች ለሚስቶቻቸው አይታመኑም፣ ብዙ ሚስቶችም ለባሎቻቸው እንዲሁ… ወዳጆች አይተማመኑም፣ መንግስት ለሕዝብ አይታመንም… ሻጭና ገዥ አይተማመኑም…

merkato-addis-ababa-copy

11) (ልመና) …

ልመና የሥራ መስክ እንጂ የችግረኞች መደጎሚያ መሆኑ እየቀረ ነው… በተስኪያን ሄዶ ስለ ገብርኤል ያለህ መስኪድ ተሰልፎ በአላህ ይልሃል… አካል ጉዳተኛውን ከጤነኛው መለየት ፈጽሞ አትችልም… ፊትን መገጣጠብና እጅ እግርን ማቆሳሰል እድሜ ለግራሶ እንጂ ቀላል ነው… አንጀት ይበላሉ እየተባሉ የሚፈበረኩት ትርክቶች እየቸኩ መጥተዋል… ምግብ እየበላህ እፊትህ መጥቶ ግትር ይልብሃል… አንዳንድ ነውረኛ የጀመርከውን ትተህ ብትሄድ ግድ አይሰጠውም… ይሉኝታ ማጣት የቢዝነሱ ሰዎች ተቀዳሚ ተግባር ነው…

File Photo

File Photo

12) (ግድ አልባነት) …

እግርህ በደረሰበት ሁሉ የግድየለሾች ተግባር ጮክ ብሎ ይጠራሃል… ታክሲ ውስጥ የተተፋ ማስቲካ ጫማህን ሲያጣብቀው፣ የመንገድ ምልክቶችን ተሸከርካሪ ሲድጠው፣ የእምዬን ስም አንዳንድ መደዴ ሲያራክሰው፣ ባለ ጥምባሆው በተዝናኖት ክብህ ጭሱን ሲያንቦለቡለው፣ አጥር ምሰሶና ግንባታን በማስታወቂያ ድሪቶ ሲያስጠይፈው፣ የቤቱን ፍሳሽ ከወንዞችና ከጎርፍ ጋር ሲቀይጠው፣ አሽከርካሪው በበጋ አቧራ በክረምት ጭቃውን መንገደኛ ላይ ሲያዘንበው፣ በታክሲ ጥቅስ ሰበብ ክብርህን ሲነካው፣ በግንባታ ሰበብ መንገድህን ሲዘጋው… ወዘተረፈ…
————————–
ይህ ሃሳብ አዋሳ፣ ድሬ፣ ባሕርዳርና ሸገር በሚኖሩ ጓደኛሞች ክርክር ላይ ተመስርቶ የተፈተለ ነው… ውይይቱ ሁሉንም አዲስ አበቤ የሚጠቀልል ፍረጃ እንዳልሆነ ልብ ይሏል… የተባለውን ካለማድረግ አልፈው ለችግሩ የመፍትሔ አካል በመሆን የተጠመዱ ብዙ ናቸውና… እናንተ ግን ምን አላችሁ?…

The post አዲስ አበባ … “አዲስም” – “አበባም” የማያደርጓት 12 ነገሮች appeared first on Zehabesha Amharic.


ኦቦ በቀለ ገርባ ታሰሩ

$
0
0

bekele Gerba OFC

(ዘ-ሐበሻ) በኦሮሚያ የተለያዩ ከተሞች የተነሳውን የሕዝብ ቁጣ ተከትሎ በርካታ ወጣቶችን እያሰረ የሚገኘው ሕወሓት መራሹ መንግስት ባለፈው ማርች 2015 ከ እስር የተፈቱትን አቶ በቀለ ገርባን እንደገና አሰረ::

ዘ-ሐበሻ ከአዲስ አበባ ምንጮቿ እንዳገኘቸው የኦሮሞ ፌዴራሊስት ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ ምክትል ሊቀመንበር የሆኑት ኦቦ በቀለ ገርባ ዛሬ የታሰሩት በኦሮሚያ የተለያዩ ከተሞች ከተከሰተው የሕዝብ ቁጣ ጋር ተያይዞ እንደሆነ ይገመታል::

ኦቦ በቀለ ከቤታቸው ሲወሰዱ በርካታ የደህንነት ሃይሎች እና ፖሊሶች እንደነበሩ ጨምሮ የደረሰን መረጃ ያስረዳል::

እንዲሁም ከአቶ በቀለ ጋር የኦፌኮ ከፍተኛ አመራር የሆኑት አቶ ደጀኔ ታፋም መታሰራቸው ተሰምቷል::

የኦሮሞ ተማሪዎች; ገበሬዎች እና ሌሎች ሕብረተሰብ ክፍሎችን የሰሞኑን ሕዝባዊ ቁጣ ተከትሎ ሕወሓት የሚመራው መንግስት በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎችን ማሰሩን ዘሐበሻ መዘገቧ ይታወሳል::

አዳዲስ መረጃዎች እንደገኘን እንመለሳለን::

The post ኦቦ በቀለ ገርባ ታሰሩ appeared first on Zehabesha Amharic.

አምስቱ የዞን ዘጠኝ ጦማሪያን ይግባኝ ተጠየቀባቸው | VOA

$
0
0

VOA Amharic |

በሽብር ወንጀል ተጠርጥረው ታስረው ፣ጉዳያቸው ለአንድ ዓመት ከአምስት ወር በላይ ሲታይ ቆይቶ ከአንዱ በስተቀር “መከላከል ሳያስፈልጋቸው በነጻ እንዲሰናበቱ” ተብሎ ከሁለት ወራት በፊት ተወስኖላቸው የነበሩት አምስቱ የዞን ዘጠኝ ጦማሪያን ይግባኝ ተጠየቀባቸው፡፡

ዘገባውን የሠራችው ጽዮን ግርማ ነች፡፡
ሙሉ ዘገባውን ከተያያዘው ድምጽ ያድምጡ፡፡

zone9

The post አምስቱ የዞን ዘጠኝ ጦማሪያን ይግባኝ ተጠየቀባቸው | VOA appeared first on Zehabesha Amharic.

ፕ/ት ባራክ ኦባማ የሟቹ ወገናችን ቤተሰቦችን በግንባር ተገኝተው አጽናኑ

$
0
0

ከታምሩ ገዳ

የአሜሪካው ፕሪዜዳንት ባራክ ኦባማ በቅርቡ( በታህሳስ 2, 2015 አ. ኤ. አ )በአሜሪካው የካሊፎርኒያ ግዛት በሰምበርላንዲኖ ክፍለ ከተማ ውስጥ ሁለት ባል እና ሚስት አሸባሪዎች የገና በአል ዋዜማን ለማክበር በተሰባሰቡ ሰላማዊ ዜጎች ላይ ባደረሱት ጥቃት አንድ ኤርትራዊ ወገናችንን ጨምሮ 14 ነጹሃን ሰዎች መሞታቸውን እና 21 መቁሰላቸውን ተከትሎ ፕ/ቱ ሰሞኑን የሟቶች ቤተሰቦችን በግንባር ተገኝተው ማጽናናታቸው ታውቋል።
ob

Obama e

obma
ባለፈው አርብ የሟቾች ቤተሰቦችን ለመጎብኘት ወደ ሰንበርላንዲኖ ጎራ ያሉት ኦባማ የሟቾች ቤተሰቦችን ከ አንድ መለሰተና ደረጃ የት/ቤት ቤተ መጽህፍት ውስጥ ለ ሶስት ሰአታት በፈጀ የተናጥል ውይይት “እግዚ አብሔር ያጸናችሁ “ በማለት ሃዘናቸውን ገልጸዋል ። የአክራሪዎቹ ሰለባዎች ከሆኑት መካከል የ60 አመቱ ኤርትራዊው የሆኑት የጤና ጥበቃ ሰራተኛው ኣቶ ይሳቅ እሚኖ የተባሉት ወገናችን ቤተሰቦችን በግንባር ያነጋገሩ ሲሆነ የሟች አቶ ይሳቅ ልጆችን ቀረብ ብለው ያነጋገሩት ኦባማ “እናንተ የይሳቅ ምትኮች (አሻራዎች ) ናችሁ”በማለት አጽናንተዋል።

የአቶ ይሳቅ ወንድም የሆኑት አቶ ሮቤል ተክለ አብ በበኩላቸው ለተለያዩ የዜና ስዎች በሰጡት አሰተያየት “የፕ/ቱ አቀራረብ ቤተሰባችንን ከዚህ ቀደም በአካል የሚያውቁ የመሰል ነበር። ወንድሜ ይሳቅ በሕይወት በነበረበት ወቅት ለፕ/ት ባራክ ኦባማ ልዩ ፍቅር እንደነበረው ይናገር ነበር ። ኦባማ በ2009 እኤአ ለፕ/ትንት ባእለ ሰሜታቸው ላይ እንዲገኝ ወንድሜ የእንግድነት ጥሪ ወረቀት ተልኮለት ነበር። ሰለ ነገ ብዙ መናገር ባልችልም ከፕ/ት ኦባማ ጋር ያደረግነው አጭር ቆይታ በጣም ገንቢ እና አጽናኝ ነበር “ብሏል። እ አኤ አ በ 2000 ለተሻለ ሕይወት ከ ኤርትራ ምድር ወደ አሜሪካ (ካሊፎርኒያ) የተሰደዱት ሟች አቶ ይሳቅ ለ 11 አመታት በጤና መኮንንት ያገለገሉ ሲሆን በ አሁኑ ወቅት የኮሌጅ ተማሪዎች የሆኑት ዮሴፍ፣ ብሩክ እና ሚልካ የተባሉት 3 ልጆቻቸውን በማሳደግ ለወግ ለማእርግ ለማብቃት ደከመኝ ሰለችኝ ሳይሉ ሲጥሩ ሕይወታቸው በድንገት የተቀጩ ታታሪ አባት እንደነበሩ የወንድማቸው /የእህታቸው ልጅ ዛኬ ገ/ኪዳን ያወሷቸዋል።

ሴት ልጃቸው ሚልካ ይሳቅ በበኩሏ ሰለወላጅ አባቷ ኣቶ ይሳቅ ስትናገር” አባቴ ርሁሩህ ሰው ነበር ። እናቴን ለምን እንዳገባት ሲነግረኝ አርሷን የመሰለች መለከመልካም እና ጥሩ ሴት ልጅ (ሚሊካን)ለማፈራት ሰለ ፈልግ በማሰብ እንደ ነበር ይመክረኝ ነበር። አባቴ ዛሬ በሁለት እግሮቼ ያለፈረሃት ቆሜ አንድሄድ ያስቻለኝ ታላቅ አባት ነበር። በማለት ሰለአባቷ ለጋሽነት፣ ግልጽነት እና የፍቅር ሰው መሆን ለ ሎሳንጀለስ ታይምስ ጋዜጣ ተናግራለች።

ይህ በዚህ እንዳለ የአሜሪካው የፈደራል የምርመራ ቢሮ(FBI) ለአቶ ይሳቅ እና ሌሎች 13 ሰላማዊ ዜጎች ሞት መንሰኤ ናቸው ያላቸው ባል እና ሚስቱ ሳይድ ሪዝዋን ፋሩክ እና ታሽፊን ማሊክ ከመቼ ጀምሮ ወደ አክራሪነት እንደተለወጡ ቁርጥ ያለ መረጃ በማሰባሰብ ላይ መሆናቸው እና መረጃውንም ለማገኘት ከወራት በላይ እንደሚፈጅባቸው ሃሙስ ታህሳስ 24 2015 ለንባብ የበቃው ሎሳንጀለስ ታይምስ ጋዜጣ ዳስሶታል።

የፈርንጆቹን የገና በአልን ከውይት ሃውስ ቤተመንግስታቸው ውጪ ለማክበር ሻንጣቸውን ከመሽንከፋቸው በፊት ከቀዳማዊት እመቤት ሚሺል ኦባማ ጋር ሃዘንተኞችን ለማጽናናት በአካል ሰምበርላንዲኖ ከተማ የተገኙት የ ልእለ ሃያሏ አገር አሜሪካ፣ ፕ/ት ኦባማ ለሁሉም ሃዘንተኛ ቤተሰቦች በጋራ ፣ በአንድነት እና በፍቅር መኖር የአሜሪካ እና የሕዝቧ ታላቁ የባሕል እሴት እንደሆነ እና በዚህም ጊዜ ሁሉም ወገኖች ለዚህ መሰሉ ድርጊት ተግባራዊነት ተግተው እንዲሰሩ ምክራቸውን እና ጥሪያቸውን አሰተላልፈዋል። በተለይ ደግሞ “ላለፉት ሁለት ሺህ አመታት የክርስቶስን መወለድ (የገና በእልን ሲያከብሩ የነበሩ የመካከለኛው ምስራቅ ዜጎች (ኢራቅ እና ሶሪያ) በአሁኑ ወቅት እራሱን የ እስልምና መንግስት እያለ የሚጠራው በአክራሪው ኢይሲስ እየደረሰባቸው ባለው ግድያ እና መዋከብ ሳቢያ የጌታ የአየሱስ ክርስቶስ መወልድን ለማብሰር ደውል እንዳይደወሉ እና ጸሎት እንዳያደርጉ የተገደዱት ክርስቲያኖችን ልናሰባቸው እና ልንጸልይላቸው ይገባል።” ሲሉ በፈርንጆቹ ገና ዋዜማ ሃሙስ እለት ላይ ከጽ/ቤታቸው የላኩት መልክት ያስረዳል።

The post ፕ/ት ባራክ ኦባማ የሟቹ ወገናችን ቤተሰቦችን በግንባር ተገኝተው አጽናኑ appeared first on Zehabesha Amharic.

Health: ሴቶች በፍቅር ውስጥ አጥብቀው የሚፈልጓቸው 6 ነገሮች |ለወንዶች ብቻ

$
0
0

ይህ የሊሊ ሞገስ ጽሁፍ በዘ-ሐበሻ ጋዜጣ ላይ ታትሟል::

 

በጥንዶች መካከል ለሚኖር የተሳካ የፍቅር ግንኙነት የፍላጎት መጣጣም እጅግ አስፈላጊ መሆኑ አጠያያቂ አይደለም፡፡ በዚህ ረገድ የሰው ልጆች በአጠቃላይ፣ ተመሳሳይ የሚመስል መሰረታዊ ፍላጎቶች ቢኖራቸውም ወንዶችና ሴቶች በየግል ከፍተኛ ቦታ የሚሰጧቸው የተለያዩ የስሜት ፍላጎቶች ይኖሯቸዋል፡፡

Love and Relationship

በግንኙነት መስክ ውስጥ ከምንጠቀምባቸው ክህሎቶች ሁሉ የመጀመሪያውና ጠቃሚ ነገር፣ የተጓዳኛችንን ጥልቅ ፍላጎት እና ተግባራት አስቀድሞ መረዳት ሲሆን፣ ይህ ማስተዋል አብሮን ያለውን ሰው ጠንቅቀን እንድንረዳ ስለሚያግዘን ችግሮች ከመሰከታቸው በፊት እንድንታደጋቸው ብሎም ከተፈጠሩ በኋላ በንቃት እና በጥበብ መለስ እንድንል ይረዳናል፡፡ አንዳንድ ጊዜ የሰዎችን መሻት ሳይነግሩን የማወቅ ክህሎትን መማርና መለማመድ፣ አታካችና አድካሚ ቢመስልም ውጤቱ ግን እጅግ አመርቂ እንደሚሆን አያጠያይቅም፡፡ አብዛኛውን ጊዜ በጥንዶች መካከል ተቀራርቦ ፍላጎቶችን ማውራት፣ ስሜትን መጋራትና ምክንያትን መግለጽ፣ የተሻለ ቅርርቦሽን በመፍጠር በትዳር ላይ መተማመንን ስለሚጨምር መልካም የሚባል ውጤትን ሊያስገኝልን ይችላል፡፡

ብዙውን ጊዜ ሰዎች ጥምረት የሚገቡት በዘርፉ በቂ የሚባል ዝግጅት ሳይኖራቸው እንደሆነ በተደጋጋሚ በዚህ አምድ ላይ የተነሳ ጉዳይ ነው፡፡ ይህም ትዳርን ውስብስብ እና አታካች እያደረገ መጥቷል፡፡ ከስልጣኔ ጋር ተያይዞ የመጣውም የሰው ልጅ ፍላጎት መጨመርና በትንሽ ነገር ያለመርካት አባዜ፣ በትዳር ውስጥ ተስፋ መቁረጥ የራሱን የሆነ ሚና ይጫወታል፡፡

በአንድ ወቅት ኖራ ሃይደን የተባለች የማህበራዊ ህይወት ተመራማሪ በመጽሐፏ እንዳለችው፣ አብዛኛው ወንዶች ስለ ሴቶች ያላቸው አተያይ እጅግ አስደንጋጭ ነበር፡፡ በወንዶች ዓይን ሴቶች ማለት፣ በዚህች ምድር ላይ ካሉ ነገሮች ሁሉ በላቀ ደረጃ እጅግ ውስብስብና፣ ፍላጎታቸው የማይታወቅ በቀላሉ የማይረኩ ፍጡሮች እንደሆኑ ይገልፃሉ፡፡

በዚሁ ጥናት ላይ የሴትን ልጅ ፍላጎት ከመረዳትና፣ ሴትን ልጅ ደስተኛ ከማድረግ ይልቅ (ኑዩክለር ፊዚክስ ማጥናት እንደሚቀል ገልጧል)

ይህ በእውነቱ ከእውነታው ጋር እጅግ የሚጣረስና ለሴቶች እጅግ አስደንጋጭ ጉዳይ ነው፡፡ ይህ እሳቤ የሚመነጨው ሁላችንም በራሳችን ግለኛ ዓለም ውስጥ ተከልለን የራሳችንን ተፈጥሮና ፍላጎት ብቻ ስለምናዳምጥና የሌሎችን ማንነት ለማወቅና ተጣጥሞ ለመኖር ምንም አይነት ጥረት ስለማናደርግ ይመስለኛል፡፡

በተለያየ ጊዜ በዘርፉ የተሰማሩ ባለሙያዎች፣ ስለወንዶችና ሴቶች ረቂቅ ባህሪያትና ፍላጎት ለማወቅ በርካታ ጥናቶችን አካሂደዋል፡፡ ከእነዚህ ጥናቶች የተውጣጣውን መደምደሚያ መሰረት በማድረግ ከ90 በመቶ በላይ የሚሆኑት ሴቶች የሚስማሙበትንና፣ ሴቶች ከትዳር አጋራቸው ወይም ፍቅረኛቸው አጥብቀው የሚሹትን 6 ነጥቦችን ከሀገራችን ነባራዊ ሁኔታ ጋር በማጣጣም ላካፍላችሁ ወደድኩ፡፡

የሴትን ልጅ ልብ ለመማረክ እና ቀጣይነት ያለው ግንኙነት ለመመስረት የሚረዱ 6 ነጥቦች

(Caring) እንክብካቤ

1. በጥናቱ ውስጥ ከተካተቱ አብዛኛዎቹ ሴቶች በፍቅር ለሚንከባከብ ወንድ በቀላሉ እንደሚሸነፉ ገልፀዋል፡፡ ይህም የሚሆነው ሴቶች በተፈጥሮ ካላቸው የእንስትነት ባህሪ የተነሳ ከወንዶች ስሜት እና ፍቅርን ብቻ ሳይሀን፣ ከለላን፣ አለኝታነትን እና እክብካቤን አጥብቀው እንደሚሹ ተናግረዋል፡፡ ይሄም ምኞት እና ደህንነት እንዲሰማው ስለሚያደርግ ህይወትን ለቀቅ አድርገው በመመልከት የበለጠ ደስተኛ ያደርጋቸዋል፡፡

2. ትኩረት

ይሄንን ፍላጎት በሁለት ከፍለን ልናየው እንችላለን፡፡

2.1 መደመጥ

Joeu Barton የተባለ የስርዓተ ፆታ ተመራማሪ በጥናቱ ላይ እንዳሰፈረው፣ ሴቶች በቀን ውስጥ በአማካኝ 20,000 ቃላቶችን ሲጠቀሙ፣ በተቃራኒው ወንዶች ደግሞ 7,000 ቃላትን በመጠቀም ሀሳባቸውን ያስረዳሉ፡፡ ይህም በግልፅ እንደሚያስረዳን አንደኛ ሴቶች ለቋንቋ እና ለንግግር ፈጣን የሆነ አዕምሮ እንዳላቸው ሲሆን፣ ሌላው እና ትኩረት ሊሰጠው የሚገባው ጉዳይ፣ ሴቶች በንግግር ራሳቸውን በመግለፅ የበለጠ ነፃነት እንደሚሰማቸው ሲሆን ችግር በገጠማቸውና በጨነቃቸውም ጊዜ በማውራት ብቻ ያለ ምንም ተጨማሪ ምክርና መፍትሄ የተሻለ እፎይታና እረፍት እንደሚሰማቸው ሲሆን፣ በዚህም ጊዜ ንግግራቸውን በትኩረት ለሚያዳምጣቸው ወንድ የተለየ ፍቅርና አክብሮት ይኖራቸዋል፡፡

2.2 አንዲሰት ሴት አብሯት ካለ ወንድ ከፍቅርና እንክብካቤ ባሻገር አትኩሮ ትሻለች

በርካታ የህይወት ተሞክሮዎች እንደሚያመለክቱት፣ ሰዎች በተሰበሰቡበት ግብዣ ላይ አንድ ወንድ ፍቅረኛውን ወይም የትዳር አጋሩን ከሰዎች ጋር በሚኖረው ጨዋታ እጇን በማሻሸት ወይም በመሳም፣ አብሮነቱን ቢያረጋግጥላት በቀላሉ ልቧን በፍቅር በማቅለጥ የጥሩ ስሜት ባለቤት እንድትሆን እንደሚረዳ ይታመናል፡፡ አብዛኛውን ጊዜ ወንዶች በግንኙነት ውስጥ የሚመለከቱት፣ ትልቁን ምስል ብቻ በመሆኑ አብሮነት በራሱ በቂ ነው ብለው ሊያስቡ ይችላሉ፡፡ ሴቶች ደግሞ ባላቸው የተለያየ አፈጣጠር ዝርዝር ነገሮች ላይ ትኩረት ስለሚያደርጉ እያንዳንዱን እንቅስቃሴና ፍሰት ይከታተላሉ፡፡ በመሆኑም ወንዶች ፍቅረኛቸው ወይም የትዳር አጋራቸውን ከመነፈጠሯም ረስተው ለረጅም ሰዓት ከሶስተኛ ወገን ጋር ጨዋታ ውስጥ ሊገቡ ይችላሉ፡፡ ይህ በሴቶች አዕምሮ ውስጥ የመተውና አትኩሮት የማጣት ስሜትን ሊያጭር ስለሚችል ወንዶች ትኩረት ሊያደርጉበት ይገባል፡፡ ይሄንን በጣም ቀላል ግን ከፍተኛ ተፅዕኖ ሊፈጥር የሚችል እውነታ በመረዳት፣ በሄዳችሁበት ሁሉ ለሴቶቻችሁ አብሮነት ትኩረትና ዕውቅናን በመስጠት፣ ስሜታቸውን ከመጉዳት ብትታደጉ በምላሹ ፍቅር እና አድናቆትን ትቀበላላችሁ፡፡

እዚህ ጋ ልብ ልንለው የሚገባው እውነታ፣ ይህ ዓለም መስጠትንና መቀበልን መሰረት ያደረገ ነው፡፡ የሰውን ስሜት ጎድቶ መልካም የስሜት ምላሽ መጠበቅ የዋህነት ስለሆነ፣ የምንፈልገውን ለማግኘት የሚፈለገውን መስጠት ግድ ይለናል፡፡

3. (Security) ጥበቃ

ከጥንት ጀምሮ ሲወርድ ሲዋረድ የመጣው፣ የወንድ ልጅ ከለላ እና መጋ መሆን፣ አሁንም ድረስ በብዙዎች ዘንድ ተቀባይነት ያለው እውነታ ነው፡፡ በዚህ በሰለጠነው እና የሴቶች እኩልነት በተረጋገጠበት 21ኛው ክፍለ ዘመን እንኳን፣ ሴት ልጅ በግሏ ገቢ በማስገኘት ሀብት ማካበት ብትጀምርም፣ የወንድ ልጅ ግብአት አቅራቢ እና ጠባቂ መሆን የሴትን ልጅ ስሜት ለማረጋጋት በጣም አስፈላጊ ነው፡፡ ከዚህም በዘለለ ወንድ ልጅ ለሴት ከተለያየ አደጋ ጠባቂ ሆኖ መገኘቱ፣ እምነቷን የበለጠ ስለሚያጠነክረው ፍቅሯ እየጎለበተ ይሄዳል፡፡

4. Blind Loyalty (ፍፁም የሆነ ተአማኒነት)

በአብዛኛው አንዲት ሴት የፍቅር ግንኙነት ውስጥ ስትሆን ወይም በወንድ ስትፈቀር ራሷን የተለየች ፍጡር አድርጋ እንድታይ ትሆናለች፡፡ ይህም ምን አልባት ከሴቶች ተፈጥሮ በተጨማሪ ወንዶች በፍቅር መብረቅ በተመቱ ጊዜ ያፈቀሯትን ሴት የግላቸው ለማድረግ የሚጠቀሙበት ገደብ የለሽ ሙገሳና ማሞካሸት፣ ሴቶች ለራሳቸው ያላቸውን አመለካከት በማዛባት፣ ውጫዊ መስህብን እንደ ብቸኛ የማንነታቸው መለኪያ አድርገው እንዲወስዱት ሳያስገድዳቸው አልቀረም፡፡

በመሆኑም በግንኙነት ውስጥ አንዲት ሴት የራሷን የመስህብ ደረጃ ጠንቅቃ ብታውቅም ባፈቀራት ወንድ እይታ ስትፈረጅ ‹‹ሁሉን ያስናቀች ቆንጆና ፀባየ ሰናይ መሆኗን እንዲነገራት ትፈልጋለች›› በማንኛውም አጋጣሚ የእሷ ወንድ የሌላዋን ቆንጆ አለባበስ ወይም አቋም ቢያደንቅ እሷን የወሰደባት ያህል ስለሚሰማት መጠንቀቅ ያስፈልጋል፡፡ በመሆኑም የሰውን ቆንጆ በመቃረም፣ የትዳር አጋራችንን ስሜት ከምንጎዳ፣ ያገባናትን ሴት በትዳር አብረን እንድንኖር ውሳኔ ላይ ያደረሰንን መልካም ሰብዕና፣ ውበት፣ ወይም ተግባር በማስታወስ ከልብ የመነጨ አድናቆታችንን እና ሙገሳችንን መቸርን ብንለማመድ፣ ለትዳራችን ዕድሜ ማራዘሚያነት እንደሚጠቅም ጥናቶች እና ተሞክሮዎች ያመለክታሉ፡፡

5. Understanding (መረዳት)

በርካታ ሴቶች ከተጓዳኛቸው አጥብቀው የሚፈልጉት ተጨማሪው ነገር፣ የትዳር አጋራቸው የእነሱን ሚና እና በቤት ውስጥ ያላቸውን አስተዋፅ እንዲረዳ እና ዕውቅና እንዲሰጥ ነው፡፡ አንዳንድ ወንዶች ሴት ልጅ በቤት ውስጥ የምታከናውናቸውን ረቂቅና እጅግ ወሳኝ ተግባራት ባለማወቅ ዕውቅናን ሲነፍጉ ይስተዋላሉ፡፡ የሴት ልጅ ተፈጥሮ ማለትም በሴትነት የምታልፋቸውን ከባባድ ደረጃዎች፣ እርግዝና፣ ወሊድ፣ ማጥባት እና ልጅን መንከባከብ በምድራችን ካለ ነገር ሁሉ እጅግ ውድ፣ ፈታኝ እና ዋጋ ሊተመንለት የማይችል መሆኑን በመረዳት፣ ሴት ሆነው ያንን መክፈል እንኳን ባይችሉ፣ ክብደቱን በመረዳት እና ርህራሄ በማሳየት ሊያዝኑላቸው፣ ሊንከባከቧቸው እና ሊደግፏቸው ይገባል፡፡ ይሄም በሴት ልጅ ልቦና ውስጥ እስከ መጨረሻው ለመቀመጥ ጥርጊያ መንገድ ይሆናል፡፡

women loves

6. Sex (ወሲብ)

በተጣማሪዎች መካከል ፍቅር ሰምሮ ኑሮ እንዲደረጅ፣ በሐሳብ እና ፍላጎት መጣጣም ተቀዳሚው መሆኑ የማያጠያይቅ ሀቅ ነው፡፡ መከባበሩ፣ መፈቃቀሩና የሐሳብ መጣጣሙ እንደተጠበቀ ሆኖ በወሲብ አለመጣጣም ባለትዳሮች ከትዳራቸው ውጪ ሌላ ሰው መጎብኘታቸው የተለመደ ተግባር እየሆነ መጥቷል፡፡

ብዙውን ጊዜ ተጣማሪዎች፣ የሐሳብ አለመጣጣምን አቻችለውና ተቻችለው ኑሮን ሲገፉ ይስተዋላል፡፡ በአሁኑ ዘመን እየተስተዋለ የመጣው እውነታ እንደሚያመለክተን ግን በወሲብ አለመጣጣምን ማስታመም ስለሚያቅታቸው ወይም ከሌላ ጋ ሲማግጡ ወይም ከነጭራሹ ትዳርን ሲያፈርሱ ይታያሉ፡፡

በአብዛኛው በርካታ ወሲብ ነክ ፅሑፎችና ጥናቶች አንድን ወንድ እንዴት ለወሲብ ማነሳሳት እንዳለብን እና እንዴት እርካታ ላይ እንዲደርስ መርዳት እንዳለብን የሚገልፁ ናቸው፡፡ ይህም የሚያሳየው የሴት ልጅ ስሜት ይሄ ነው የሚባል አትኩሮት ከማህበረሰቡ ጭምር እንዳልተቸገረው ነው፡፡

Nora Hayden (How to satisfy a women every time) በተሰኘው መጽሐፏ ላይ እንደገለፀችው 80% የሚሆኑት ሴቶች፣ እውነተኛ እርካታ ላይ እንደሚደርሱ ሆኖም የትዳር አጋራቸውን ለማስደሰት ሲሉ ብቻ እርካታ ላይ እንደደረሱ እንደሚያስመስሉ ይናገራሉ፡፡ ይህም የሚሆነው ወንዶች በወሲብ ጊዜ የሴትን ልጅ ፍላጎት እና የስሜት  ምስጢር መረዳት ስለሚያቅታቸው እነሱ በሚረኩበት መንገድ ይረካሉ ብለው በማሰብ ዘልማዳዊ የሆነውን ግንኙነት ያደርጋሉ፡፡ ሆኖም ፈጣሪ ወሲብን በትዳር መካከል እንድትደሰትበትና ትውልድን እንድናስቀጥልበት የሰጠን ታላቅ ፀጋ በመሆኑ፣ የሴትም ልጅ ስሜት መጠበቅ እና በባሏ መደሰት እንዳለባት በመረዳት በግልፅ በመወያየትም ሆነ በዘርፉ የተፃፉ ጽሑፎችን በማንበብ፣ ደስታውን የጋራ የማድረግ የወንዶች ተቀዳሚ ኃላፊነት ነው፡፡

በመጨረሻ ማንሳት የምፈልገው ነጥብ፣ ብዙዎች በትዳር ላይ በግንኙነት ዙሪያ በመርህ ደረጃ የሚነሱ ጠቃሚ ምክሮችን ማንበብ ፋይዳ ቢ መሆኑን ሲናገሩ ይታያል፡፡ ለዚህም እንደ ምክንያትነት የሚያነሱት መከራከሪያ የፀሐፊዎቹ  ወይም አነበብን የሚሉ ሰዎችን ግለ ህይወት በናሙናነት በማንሳት፣ በትዳር ህይወታቸው ስኬታማ አለመሆናቸውን ነው፡፡ እዚህ ጋ መረዳት ያለብን ቁም ነገር፣ ችግሩ ያለው ከዕውቀቱ ወይም ከንባቡ ሳይሆን ያወቅነውን እና የሰማነውን በልቦናችን አኑረን መተግበር ስለሚሳነን መሆኑን ነው፡፡ በመሆኑም ተፈጥሮ የለገሰችን ሰብዕና፣ በህይወት ተሞክሮ እና ዕውቀት በማዳበር፣ ያካበትነውን ዕውቀት በመተግበር እና ለውጥ በማምጣት ትዳራችን በግምት ሳይሆን፣ በጥበብ የምንመራትን ልቦና ይስጠን፡፡

ሴት ልጅ ምን መስማት አትሻም!

ሴቶች ስለ ሌላ ሴት ወይም ስለ ቀድሞ ጓደኛህ ስታደንቅ መስማት አትፈልግም፡፡ ከሌላ ሴት ጋር እንድታወዳድራትም እንዲሁ፡፡ ስለ ሰውነት ቅርጽና ውበቷ አድናቆት እንጂ ነቀፌታ ቅር ያሰኛታል፡፡ በድንገት ተሳስተህ የሌላ ሴት ስም ማንሳትም አይኖርብህም፡፡ በሌላ መንገድ ያስጠረጥርሃልና፡፡ ከአሁን ቀደም በነበረህ የሴት ልጅ ትውውቅ ውስጥ አላግባ ያደረካቸውን ነገሮች ማውራትህ ከባድ ግምት ውስጥ ይጥልሃልና በተቻለ መጠን ከኋላ ፈቅር ታሪክህ ውስጥ ጥሩ ጥሩውን እንጂ የሚያስተችህን ለመርሳት ወይም ላለማንሳት ጥረት አድርግ፡፡ በሌላዋ ላይ ይህን ያደረገ በእኔም ላይ ማድረጉ አይቀርም የሚል እምነት ይኖራታልና፡፡ ሴቶች ስለ አንተ ማወቅ የሚፈልጉትን ሲጠይቁህ እውነቱን መናገሩን ብቻ ነው የሚያዋጣው፡፡ ብዙ ጊዜ ሴቶች ለማወቅ በሚመስል መልኩ ይጠይቃሉ እንጂ የሚጠይቁትን ነገር ቀድሞውኑ ያውቁታልና አትዋሽ!

በተቻለ መጠን ከአሁን ቀደም ከነበረህ የፍቅር ትስስር እንዴት እንደተለያየህ ምክንያትህን አሳማኝነት ያለውና ከአንተ በኩል ከፍተኛ ጥረት ማድረግህ ላይ ያነጣጠረ ይሁን እንጂ ኃላፊነትህን ስላለመወጣትህ የሚያንፀባርቁ ምክንያቶችን ወይም ደግሞ ቀድሞውኑ ለመለያየት የማያበቁ ምክንያቶችህን ሴቶች መስማት አይፈልጉም!! ቢሰሙም ትዝብት ውስጥ ይጥሉሃልና ጠንቀቅ በል!!

The post Health: ሴቶች በፍቅር ውስጥ አጥብቀው የሚፈልጓቸው 6 ነገሮች | ለወንዶች ብቻ appeared first on Zehabesha Amharic.

ጋዜጠኛ ጌታቸው ሽፈራው ታሰረ

$
0
0

(ዘ-ሐበሻ) የነገረ ኢትዮጵያ ጋዜጣ አዘጋጅ ሆኖ በሃገር ቤት መረጃን ለሕዝብ ሲያደርስ የቆየው ጋዜጠኛ ጌታቸው ሽፈራው ዛሬ በደህንነት ኃይሎች ታፍኖ ተወስዶ መታሰሩ ተሰማ:: ከሃገር ቤት የመጡ መረጃዎች እንደሚያመለክቱት ሕወሓት የሚመራው መንግስት ሰሞኑን ከአዲስ አበባ ማስተር ፕላን ጋር ተያይዞ በተነሳው የሕዝብ ቁጣ በመደናገጥ በርካታ አክቲቭስቶችን እያሰረ ይገኛል::

gEtacew shiferaw

ኦህዴድን ጥርስ ያለው አንበሳ በማስመሰል በየሚዲያው እንዲነገር በማድረግ ሕዝቡን ያደናገረው ሕወሓት የሚመራው መንግስት በተለይ ሰሞኑን በኦሮሚያ የተነሳውን የሕዝብ ቁጣ ለማረጋጋት የኦህዴድ ባለስልናት እንደ አባዱላ ገመዳ ያሉት በየሚዲያው በማቅረብ የመንግስትን ፖሊሲ እንዲተቹ በማድረግና ከሕዝብ ጎን እንደቆሙ በማስመስል ፕሮፓጋንዳቸውን ከሰሩና ሕዝብን የማረጋጋት ሥራ በኋላ ቀስ በቀስ አክቲቭስቶችን ማሰራቸውን ቀጥለዋል::

ትናንት አቶ በቀለ ገርባ የታሰሩ ሲሆን እስካሁን ድረስም ከ3000 በላይ ሰው በዚሁ በኦሮሚያ ከተቀሰቀሰው የሕዝብ ቁጣ ጋር ተያይዞ ታስረዋል::

ጋዜጠኛ ጌታቸው ሽፈራው መንግስትን በፌስቡክ እንዲሁም በነገረ ኢትዮጵያ ጋዜጣ ደባውን ሲያጋልጥ የቆየ ሲሆን በመጨረሻም ከቤቱ ወደ ሥራ ሊሄድ ሲውጣ ደህነነቶች እና ፖሊሶች አፍነው ወስደው ማዕከላዊ አስረውታል::

በሌላ በኩልም የሰማያዊ ፓርቲ አባላት የሆኑት ቴዎድሮስ አስፋው ከቤቱ እንዲሁም አቶ ዳንኤል ተስፋዬ ከፍርድ ቤት ታፍነው ተወስደው ታስረዋል::

The post ጋዜጠኛ ጌታቸው ሽፈራው ታሰረ appeared first on Zehabesha Amharic.

Viewing all 15006 articles
Browse latest View live