Quantcast
Channel: Ethiopian News | ዘ-ሐበሻ | Latest News Provider | News For All
Viewing all 15006 articles
Browse latest View live

የአዲስ አበባ ህፃናት ከቆሻሻ ላይ ምግብ አንስተው ሲመገቡ የሚያሳይ ቪዲዮ |ከተሜው ከተራበ ቆይቷል

$
0
0


ስሜነህ ከሚኒሶታ

15 ሚሊዮን ሕዝብ ተርቧል ሲባል አንዳንድ የስርዓቱ ገጽታ እንዲበላሽ የማይፈልጉ ተላላኪዎች “የተራበም በርሃብ የሞተም የለም” በሚል አይናቸውን ጨፍነው ሲከራከሩ ማየት በጣም ያማል:: በቅርቡ በቢቢሲ ላይ ወጥታ ልጇ በርሃብ የሞተባት ወ/ሮ ብርቱካን እንዴት አድርገው በመሳሪያ ሃይል አስፈራርተው ልጄ በርሃብ አልሞተም እንድትል እንዳደረጓት የቀናት ት ዝታችን ነው:: ዛሬ ከዓመት በፊት በኢትዮጵያ የተለቀቀውን ቪዲዮ ለትውስታ ያቀረብኩላችሁ እነዚሁ የ ስር ዓቱ መልካም ገጽታ ገንቢዎች እንዲያፍሩ በማሰብ ነው:: አሁን ድረስ በአዲስ አበባ ችግር ውስጥ ያሉ ህፃናት ከቆሻሻ መጣያ ምግብ እያነሱ ይመገባሉ:: የ ስር ዓቱ ተላላኪዎች እነዚህንስ ምን ይሏቸው ይሆን?

የሚያሳዝነው የስርዓቱ ደጋፊዎች ይህን እውነታ ለመደበቅ መሞከራቸው ብቻ ሳይሆን ሌሎች ሃገር ወዳድ ኢትዮጵያውያን ይህን ለመለወጥ ሲሰሩና ሲጥሩ አላሰራ ማለታቸው ነው:: በቅርቡ በየሃገራቱ ያሉት የኢትዮጵያ ኢምባሲዎች ያወጧቸውን መግለጫዎች ይጠቅሷል::

addis ababa

The post የአዲስ አበባ ህፃናት ከቆሻሻ ላይ ምግብ አንስተው ሲመገቡ የሚያሳይ ቪዲዮ | ከተሜው ከተራበ ቆይቷል appeared first on Zehabesha Amharic.


የህዝበ ሙስሊሙ ወኪሎች ከከፍተኛ የአሜሪካ የዉጭ ጉዳይ መቤት ልኡካን ጋር መገናኘታቸዉ ታወቀ

$
0
0

(ቢቢኤን ራድዮ) የኢትዮጵያ መንግስት በሙስሊሙ ማህበረሰብ የእምነት ጉዳዮች በይፋ ጣልቃ መግባቱን ተከትሎ ህዝበ ሙስሊሙ በድምጹ የመረጣቸዉ የህዝብ ወኪሎች በአለም አቀፍ ደረጃ ተጽእኖ መፍጠራቸዉ የሚታወቅ ነው። በአይነቱ ልዩ የሆነንን የሰላማዊ ትግል ዘይቤን የቀየሱት የህዝበ ሙስሊሙ ወኪሎች፤ በኢትዮጵያ መንግስት የደህንነት ባለስልጣናት ለከፍተኛ መከራና ስቃይ መዳረጋቸዉ የሚዘነጋም አይደለም። ከማእከላዊ የማሰቃያ ግዞት ጀምሮ በቂሊንጦና በቃሊቲ እስርቤቶች ዉስጥ ያለፉት የህዝበ ሙስሊሙ ወኪሎች ሰላምን በመስበካቸዉ እስከ 22 አመት በሚደርስ ጽኑ እስራት እንዲቀጡ ካንጋሮ በሚባለዉ ፍርድ ቤት ተበይኖባቸዋል።

የሙስሊሙ መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ አባላት ወኪሎች ከዞን 9 አባላት ጋር (Photo BBN)

የሙስሊሙ መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ አባላት ወኪሎች ከዞን 9 አባላት ጋር (Photo BBN)

የነዚህን የህዝብ ወኪሎች ንጹህነትና የሰላም አምባሳደርነት አያሌ መንግስታዊ እና መንግስታዊ ያልሆኑ ተቋማት በመመስከር በነጽ መለቀቅ አለባቸዉ ሲሉም ድምጻቸዉን በይፋ እያሰሙ ይገኛሉ።

የህዝበ ሙስሊሙ ሰላማዊ ትግል ከጅመረበት ጀመሮ በህዝበ ሙስሊሙ ላይ የሚደርሰዉ በደል የሚዘግበዉ የ አሜሪካ የዉጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት የኢትዮጵያ መንግስት በተለያዩ አጋጣሚዎች በሚወስዳቸዉ እርምጃዎች ስጋት እንዳለዉ በመግለጫ ቢገልጽም ከጨቋኙ የኢትዮጵያመንግስት ጋር በዲፕሎማሲያዊ አሰራር ያብራል የሚል ትችት ይቀርብበታል።
usa
ወደ አዲስ አበባ ክፍተኛ የሉካን ቡድን የላከዉ የ አሜሪካ የዉጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት ከህዝበ ሙስሊሙ ወኪሎች ከኡታዝ ያሲን ኑሩ፣ ከሳቢር ይርጉና ከህግ አማካሪዎቻቸዉ ጋር በመገናኘት ወሳኝ በሆኑ ጉዳዮች ላይ መወያየቱን ቢቢኤን ለማወቅ ችሏል። በሜሪካዉ የዉጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ጃን ኬሪ የተላኩትና ከህዝበ ሙስሊሙ ወኪሎች ጋር የተገናኙት የመስሪያቤቱ ከፍተኛ ባለስልታናት የዲሞክራሲና፣የሰብዓዊ መብትና የሰራተኞች ዱዳይ ረዳት ሴክረታሪ፣ራልፍ ኦልሰን የአፍሪካ ጉዳዮች ዳይሬክተርና ሮዝ ጃክሰን የዲሞክራሲ፣ የሰብዓዊ መብትና የሰራተኞች ጉዳይ ሐላፊ ናቸዉ።

እነዚህን የህዝብ ወኪሎች የኢትዮጵያ መንግስት ማእከላዊ አስገብቶ በቶርቸር ያሰቃያቸዉና ደህንነቶች ይቆታጠሩታል በሚባለዉ ፍርድ ቤት እስከ 22 አመት ጽኑ እስራት የፈረደባቸዉ ቢሆነም የአሜሪካ መንግስት የዉጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት (ሚኒስቴር) በሙሉ እዉቅናና ክብር እንደ ህዝብ ወኪል እነርሱን ማናገሩ የኢትዮጵያ መንግስትን ፍረጃ ዉድቅ የሚያደርግ የዲፕሎማሲ እርከን ነዉ በማለት አስተያየት እየተሰጠበት ነዉ። ሌሎቹም አእስር ላይ የሚገኙት የህዝብ ወኪሎች መፍትሔን ለማፈላለግ ህዝብ ዉክልና የሰጣቸው በመሆናቸዉ ነጻነታቸዉን በይፋ ተቀዳጅተዉ በመሰል አገራዊና ዲፕሎማሲያዊ ጉዳዮች ላይ አምባሳደር ሆነዉ የሚሰሩበት ቀን እሩቅ አይደለም።ሁሉም በአቅሙ፣ሁሉም በችሎታዉ ተጠናክሮ መስራት አለብት ተብሏል። በተለይም በዋሽንግተን ዲሲና በአካባቢዋ ያሉ ኢትይጵያዉን ለዚህ ዲፕሎማሲያው ተሞክሮ ያደረጉት አስተዋ የላቀ በመሆኑ ጥረታቸዉ ሊቀጥል ይገባል የሚል ገንቢ አስተያየት አለ።

The post የህዝበ ሙስሊሙ ወኪሎች ከከፍተኛ የአሜሪካ የዉጭ ጉዳይ መቤት ልኡካን ጋር መገናኘታቸዉ ታወቀ appeared first on Zehabesha Amharic.

ለ ፕ/ር  ኤፍሬም ይስሀቅ –  ይገረም  ዓለሙ

$
0
0

እውነትን   የምታውቁ ፤ ውሸትም  ሁሉ  ከእውነት  እንዳልሆነ  ስለምታውቁ  እንጂ  እውነትን  ስለማታውቁ  አልጽፍላችሁም፡፡  የሐዋርያው  ዮሐንስ  መልዕክት  1 .. 2.. 21

ሰሞኑን ፕ/ር ኤፍሬም ይስሀቅን ፎቶ ግራፋቸውንና ስማቸውን በአንዳንድ ድረ ገጾች ሳይ  አስር ዓመታት ያስቆጠረውና  የረሳሁት የመሰለኝ በርሳቸው ላይ የነበረኝ ቅሬታ ተቀሰቀሰብኝ፡፡ ለካስ ነገርም እንደ እሳት ተዳፍኖ የጠፋ መስሎ ይኖርና  የሚገልጠው ነገር ሲያገኝ ትርክክ ያለ ፍም ሆኖ ያቃጥላል፡፡

ፕ/ር ኤፍሬም ከወያኔ ጋር ያላቸው ትውውቅ መቼ የትና እንዴት እንደጀመረ ባይታወቅም ገና የወያኔ ሥልጣን ባልረጋ  ባልተረጋጋበትና አቶ ታምራት ላይኔ ጠቅላይ ምኒስትር በነበሩበት ወቅት ከአንድ ወርሀዊ መጽሄት ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ ለአይኔ ታምር አየሁ ብለው በተቀኙበት ወቅት ነው ያወኩዋቸው፡፡

ከዛ በኋላ በምርጫ 97  የወያኔ ሥልጣን ወይንም ሞት ዓላማ የፈጠረውን  የፖለቲካ ትኩሳት ለማብረድ ከአሜሪካ አዲስ አበባ በየወሩም በየሳምንቱም ሲመላለሱ በኋላም ጥረታቸው ውጤት አግኝቶ የቅንጅት አመራሮችንና ሌሎችንም በምርጫ 97 ምክንያት የታሰሩ ሰዎችን ማስፈታት በመቻላቸው  የመገናኛ ብዙኃን ትኩረት ሆነው ነበርና ያኔ ይበልጥ አውቅናቸው፡፡

ቅንጅቶችን በማሰሩም በመክሰሱም በማስፈረዱና ይቅርታ አስጠይቆ በመልቀቁም ብቸኛ ተዋናይ የነበሩት አጼ በጉልበቱ አባ መላ ጠቅላይ መንግሥት መለስ ዜናዊ  በአንድ በኩል  ከዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ከሚሰነዘሩ ጥያቄዎችና  ጫናዎች ለመገላገል በሌላ በኩል  በሸህ አላሙዲን አዳራሽ ተገኝተው ከባለቤታቸው ጋር የደነሱበትን የሚሊኒየም በአል በተረጋጋ ሁኔታ ለማክበር ቅንጅቶችን መፍታት ነበረባቸው፡፡ ይህ ደግሞ ዝም ብሎ የሚሆን አይደለምና  የወንድ በር ለማግኘት አንድ ድራማ አዘጋጁ፡፡ በመሪ ተዋናይነትም  ፕ/ር ኤፍሬም ይስሀቅን መረጡ፡፡ ፕ/ር ኤፍሬምም ያን ድራማ በተገቢው መጫወታቸውን የተመለከተው ሁሉ የሚያረጋግጠው ነው፡፡

በዛን ወቅት ከታየ ከተሰማው  በሁለት ነገር ፕ/ር  ኤፍሬምን አደንቃቸዋለሁ አመሰግናቸዋለሁም፡፡ የመጀመሪያው መሪ ተዋናይ ሆነው እንዲጫወቱበት የተዘጋጀው ድራማ በማንም የጻፍ በማንም ይዘጋጅ፤ በመድረክ ከሚታየው የተለየ ድብቅ ዓላማም ይኑረው ከአሜሪካ አዲስ አበባ ከቤተ ምንግሥት ቃሊቲ ( አንዳንዴ በቀን ሁለቴ) እየተመላለሱ የቅንጅት አመራሮችን ብቻ ሳይሆን በርካታ እስረኞችን ከወህኒ ለማስወጣት ችለዋልና ነው፡፡ (በዚህ ሽልማት እንዳገኙም ይታወሳል፡፡ ሁለተኛው ምንም እንኳን የፈለጉት ባይሳካምና የተናገሩት ተግባራዊ ባይሆንም አቶ መለስን እስር ቤቶች በሙሉ ይዘጉ እያልኩ እየጠየኩዋቸው ነው  ብለው ነበርና ( ከዚህ ያለፈ የማድረግ አቅሙ የላቸውምና) ማሰባቸውና መናገራቸው ብቻውን ያስመሰግናቸዋል፡፡(ይዘጉ ያሉዋቸው እስር ቤቶች ዛሬ እየሰፉና እየተስፋፉ መሄዳቸውን ያውቁ ይሆን)

ephrem yisak

የተከፋሁባቸው ያፈርኩባቸውና ያዘንኩባቸው  ጉዳይ ግን ግዙፍ ነው፡፡ እሱም ነው ስምና ፎቶአቸውን ድረ ገጾች ላይ ተቀስቅሶ   ይህችን አስተያየት እንድጽፍ ያበቃኝ፡፡ በእድሜም ሆነ በእውቀት የገፉ በየንግግራቸው ጣልቃ ከመጽኃፍ ቅዱስ በመጥቀሳቸውም ሆነ  በአለባበሳቸው  እግዚአብሄርን አማኝ መሆናቸው የሚታወቅ ሰው ርሳቸው በመሪ ተዋናይነት የተጫወቱበት ድራማ ምክንያት ሆኖ ወ/ት ብርቱካን ዳግም ስትታሰር  እንዴት እውነቱን መናገርና  የተጫወቱትን ገጸ ባህርይ  መግለጽ ተሳናቸው ነው ቅሬታየ፡፡

ሌሎች ማስረጃዎችን ትተን  ቅንጅቶች በተፈቱበት ዕለተ አርብ  ሐምሌ 13/1999 ዓም  “ከፕ/ር ኤፍሬምና ከሀገር ሽማግሉዎች የተሰጠ መግለጫ ” ተብሎ ፕሮፌሰሩንና ቀሪዎቹን ሽማግሌዎች ሁለት የተለያዩ አካላት አድርጎ ገልጾ የወጣውንና ሙሉ ቀን በመንግሥት መገናኛ ብዙኃን ሲተላለፍ የዋለውን  መግለጫ መለስ ብለን ብናስታውስ ቅንጅቶች የተፈቱት በህግ አግባብ ሳይሆን በሽምግልና ለመሆኑ   እንዲህ በማለት ያረጋግጥልናል፡፡

“ ምርጫ 97 ተከትሎ በሀገራችን በተፈጠረው አለመግባባት ምክንያት ለችግሩ ሰላማዊ እልባት እንዲገኝ በአገራዊ ወግ መሰረት መፍትሄ ለማፈላለግ ለ18 ወራት ያህል ጥረት ስናደርግ ቆይተናል… ለክቡር ጠቅላይ ምኒስትር መለስ ዜናዊ አመራር ቅንነትና አርቆ አስተዋይነት በአድናቆትና በትህትና እናመሰግናለን… እስረኞቹም የቀረበውን ሀሳብ ተቀብለው የምህረት ጥያቄ እንዲሳካ በማድረግ ጥረታችን ውጤታማ ይሆን ዘንድ ለሰጡን በጎ ምላሽና ላሳዩን ክብር በፈጣሪ ስም እናመሰግናለን” ይላል መግለጫው፡፡

ወ/ት ብርቱካን ከእር ቤት ወጥታ የአንድነት ፓር ሊቀመንበር ከሆነች በኋላ ስዊድን ሀገር ሄዳ በካሄደችው ስብሰባ ላይ ከእስር ስለወጡበት ሁኔታ ተጠይቃ የሰጠችው ምላሽ እነ ፕ/ር በመግለጫቸው ከገለጹት ምንም የተለየ ነገር አልበረውም፡፡ የህግ ባለሙያ እንደመሆኗ የይቅርታ አፈጻጸም ህግን እንደምታውቅ ገልጻ ከእስር የወጡት በዛ መንገድ ሳይሆን በሽምግልና መሆኑን ነው የተናገረችው፡

ይቺ ባቄላ ካደረች አትቆረጠምም የሚለው ወያኔ ግን ይህን ሰበብ አድርጎ ይቅርታዋን አንስቼአለሁ ብሎ መልሶ ወደ ነበረችበት ቃሊቲ ሲያስገባት ዋንኛው ተዋናይ ፕ/ር ኤፍሬምም ሆኑ የሽምግልናው ቡድን አባል ተብለው በቴሌቪዥን ያየናቸው ትልቅ ስም ያላቸው  ሰዎች አንዳቸውም አንድም ቃል አለመተንፈሳቸው አሳዛኝ ነበር፡፡ በርግጥ የሽምግልናውን ሂደት ከአቶ መለስና ከፕ/ሩ በስተቀር ሌሎቹ ያወቁ ነበር ብሎ መገመት ይቸግራል፡፡ መግለጫውም እኮ ከፕ/ር ኤፍሬምና ከሀገር ሽማግሌዎች ተብሎ ሲጻፍ ለማስተላለፍ የተፈለገው መልእክት ኖሮ እንጂ በችኮላ የተሰራ ስለሆነ የሚሰጠው ትርጉም ሳይታሰብበት ነው ሊባል አይችልም፡፡

በኋላ አቶ መለስ ብርቱካንን ለሁለተኛ ግዜ ካሳሰሩ በኋላ ለእስሩ የሚሰጡት ምክንያት ፈጽሞ የተምታታ መሆን ለድርጊቱ ህገ ወጥነት አንድና ዋና ማሳያ ነበር፡፡ ከብዙዎቹ በአቶ መለስ አንደበት ከተነገሩ ምክንያቶች መካከል አላስተባብልም በማለታቸው ነው፤ይቅርታ አልጠየኩም በማለታቸው ነው፤ቅድመ ሁኔታ በመጣሳቸው ነው የሚሉት ይጠቀሳሉ፡፡ ከዚህም አልፈው  ከታሳሪዎቹ ጋር ሽምግልና ብሎ ነገር አልነበረም ብለው ሽምጥጥ አድርገውም ክደዋል፡፡ ይህ ሁሉ ሲባል ሌላው ቢቀር ፕ/ር ኤፍሬም ሽምግልናማ ነበር ብሎ ለማናገር ያለመቻላቸው ከፈጣሪ በላይ የአቶ መለስ ወዳጅነት በልጦባቸው፤ ርሳቸውም እንደሌሎቹ ከመንፈሳዊው ተግባር ይልቅ ለስጋቸው አድልተው ወይንስ ፈርተው የሚለው እስከዛሬም ምላሽ ያላገኘ ጥያቄ ነው፡፡ ይህን ጥያቄ ሳይመልሱት ሞት ከቀደማቸው ደግሞ ጥሩም ሆነ መጥፎ ስራ በየመልኩ ከመቃብር በላይ ይነሳል ይወሳልና ይከተላቸዋል፡፡ እናም የርሳቸው እውነቱን መናገር ትናንት በሆነው ላይ የሚያመጣው ለውጥ ባይኖርም ለዛሬም ሆነ ለነገ ጠቀሜታ አለውና ሞት ሳይቀድማቸው ይንገሩን፡፡ ከምንም በላይ ደግሞ ለርሳቸው ከህሊና እዳ መገላገል ነው፡፡

በዚሁ አጋጣሚ የቀድሞው ፕሬዝዳንት ግርማ ወልደጊዮርጊስም  ሞት ሳይቀድማቸው በፊት ነግረውን መሄድ ቢችሉ አንድ ጥያቄ ላቅርብ፡፡ ይቅርታ መስጠትም ሆነ የተሰጠን ይቅርታ የማንሳት ሥልጣን በህገ መንግሥቱ የተሰጠው ብቸኛ ሰው  ሰው የሀገሪቱ ፕሬዝዳንት ነው፡፡ ይህን ሲያደርግ የሚከተለው ደግሞ የይቅርታ ሥነሥርዓት አዋጁን ነው፡፡ብርቱካን ይቅርታዋ ተነስቷል ተብሎ ዳግም የታሰረችበትን ሁኔታ የሚደግፍ አንድም አንቀጽ በአዋጁ ውስጥ ያለመኖሩ በወቅቱ በስፋት የተነገረ ጉዳይ ነው፡፡ ታዲያ አቶ ግርማ ምን አይተው በምንስ ላይ ተመስርተው የወ/ት ብርቱካን ይቅርታ ተነስቶ ዳግም እንድትታሰር በፊርማዎ አጸደቁ? ወይንስ ርስዎም እንደማንኛውም ሰው በመገናኛ ብዙኃን ከመስማት ውጪ የሚያውቁት ነገር አልነበረም፡፡ ይህችን አለም ከመሰናበትዎ በፊት እውነቱን ይንገሩን፡፡ለንስሀም ይሆንዎታል፡፡

የብርቱካን ዳግም እስር ህጋዊ መሰረት የሌለው መሆኑን ገልጸው የጻፉና ከአሁኑ የኮሙኒኬሽን ምኒስትር ጌታቸው ረዳ ጋር በአዲስ ነገር ጋዜጣ የብዕር ጦርነት ገጥመው በድል የተወጡት ዶ/ር ዳኛቸው አሰፋ ነበሩ፡፡ «ብርቱካንን መንገድ በመንሳት ወይንስ ይቅርታ በማንሳት» በሚለው ለአቶ ጌታቸው ምላሽ በሰጡበት  የመጋቢት 12/2001 ዓም ጽሁፋቸው « በእኔ እምነት መንግስት ወ/ት ብርቱካን የተቀበለችውን ይቅርታ አለማንሳቷን መቀበል ያልፈለገበት ምክንያት በሽምግልና ከተገኘ ይቅርታ ይልቅ በህግ ሂደት ለተገኘ ይቅርታ ይበልጥ ክብደት ስለሚሰጥ ነው፡፡ ለምሳሌ በሙግት ላይ ያለ አንድ ሰው ጉዳዩ በህግ አለቀልኝ ሲል እና በሽምግልና አለቀለኝ ሲል ያለው ትርጉም የተለያየ ነው፤በሕግ አለቀልኝ ሲል የሕጉ መንገድ ፍጹማዊ እና ብቸኛ ድል ማገኘቱን የሚያሳይ ሲሆን በሽምግልና አለቀልኝ ሲል ደግሞ በድርድር በውይይትና በመቻቻል ብያኔውን ማግኘቱን ያሳያል፤መንግስትም በሽምግልና የተገኘውን ይቅርታ ትቶ ብቸኛና ፍጹመዊ ድል ያጎናጽፈኛል ብሎ የሚያምንበትን በህግ ሂደት የተገኘ ይቅርታ የሚመርጥ በመሆኑ ወ/ት ብርቱካን የተቀበለችውን ይቅርታ ያለማንሳቷን ማረጋገጫ ቃል አልተቀበለም» በማለት ነበር የዳግም እስሩን ምንነትና የነገሩን ምክንያት የገለጹት፡፡

የሽምግልናው ዋንኛ ተዋናይ የነበሩትና በዚሁ ተግባራቸው ለሽልማት የበቁት ፕ/ር ኤፍሬም ግን 18 ወራት የፈጀ የሀገር ሽምግልና ጥረታችን ውጤት አገኘ ብለው አቶ መለስንና በሽምግልና ከእስር የተፈቱትን ለሽምግልናው ስኬት አመስግነው መግለጫ አንዳላወጡ በየመገናኛ ብዙኃኑ በኩራት እንዳልተናገሩ ሁሉ ይሄ ሁሉ በአቶ መለስ ተክዶ ሰው ለእስር ሲዳረግ ዝም አሉ፡፡እግዜአብር ግን ያያል፡፡ስለሆነም ፕ/ር ኤፍሬም አንድም አሁን አቶ መለስ ስለሌሉ ሁለትም ተፈጥሮአዊ ነውና ሞት የማይቀር በመሆኑ ከመሰናበትዎ በፊት እውነቱን ይነግሩን ዘንድ በሚያምኑበት አምላክ ስም እጠይቀዎታለሁ፡፡ እውነትን ደብቆ ለንስሀ ሞት መብቃት ይቻል ይሆን!

 

 

The post ለ ፕ/ር  ኤፍሬም ይስሀቅ –  ይገረም  ዓለሙ appeared first on Zehabesha Amharic.

“በአማራ ብሄር ተወላጅ ወገኖቻችን በቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል እየደረሰባቸው ያለው ዘግናኝ ጭፍጨፋ ኣጥብቄ እኮንናለው”አምዶም ገብረሥላሴ

$
0
0

ይህ ዜጎች ባገራቸው ይህ የመሰለ ጭፍጨፋ መካሄዱ እጅጉን የሚያሳዝንና የሚያሳፍር ሰብኣዊነት የጎደለው ተግባር ነው።
መንግስት ለዚህ ኣስደንጋጭና ዘግናኝ ተግባር ሃላፍነት በመውሰድ ወንጀሉ በኣስቸኳይ እንዲያስቆመውና ወንጀለኞች ለፍርድ እንዲቀርቡ ማድረግ ኣለበት እላለው።

(ከዚህ ቀደም ከጉራ ፈረዳ የተፈናቀሉ አማሮች፡ ፎቶ ፋይል)

(ከዚህ ቀደም ከጉራ ፈረዳ የተፈናቀሉ አማሮች፡ ፎቶ ፋይል)


ዜጎቻችን በስደት ሳውዲ ዓረብያ፣ የመን፣ ደቡብ ኣፍሪካ፣ ሊብያ፣ ደቡብ ሱዳንና ቤሩት የመሳሰሉ ሃገራት፤ በቀይ ባህር፣ ሜድትራንያን ባህር፣ በሲናይና ሰሃራ በረሃዎች እየደረሰባቸው ያለው መቅዘፍት ሳይበቃ በገዛ ሃገራቸው ይህን የመሰለ ሰቅጣጭ ጭፍጨፋ ሊደርስባቸው ኣይገባም።

ሃገራችን 15 ማልዮን በኣስከፊ ረሃብ በያዘበትና ሂወቱ እያጣበት ባለበት ግዜ ይህን መሰል ወንጀል መፈፀሙ የሚዘገንን ብቻ ሳይሆን የሚያሳፍር ወንጀል ነው።

ብኣዴንም እወክለዋለውና ኣስተዳድረዋለው የሚለው ህዝብ ኣስከፊ ወንጀለ እየተፈፀመበት እያየ የሰው መሰውያ እንደለመደ ጣኦት ምንም ሳይል ደማቅ በዓል እያሳለፈ መሆኑ ያስገርማል።
የኢህኣዴግ መንግስትም እንደዚህ ዓይነቶች ወንጀሎች የሚፈፅሙ ወንጀለኞች ይዞ ለፍርድ የማያቀርብ ከሆነ ኣስፍኘዋለው የሚለው ሰላም ከመደፍረሱ በላይ የወንጀሉ ተባባሪና ቁጥር ኣንድ ተጠያቂ ያደርገዋል።
መንግስት ወንጀለኞች ባስቸኳይ ለህግ ያቅርብልን !

The post “በአማራ ብሄር ተወላጅ ወገኖቻችን በቤንሻንጉል ጉምዝ ክልል እየደረሰባቸው ያለው ዘግናኝ ጭፍጨፋ ኣጥብቄ እኮንናለው” አምዶም ገብረሥላሴ appeared first on Zehabesha Amharic.

ዛሬ 500 ቀናት በእስር የሚሞላው የወኅኒ ጓደኛዬ ትዝታ |በፍቃዱ ዘ ኃይሉ

$
0
0

‹‹…ይወስዳል መንገድ፣ ያመጣል መንገድ
አንድ የሚጠላ፣ አንድ የሚወደድ…››

ሕይወት መንገድ ነች፡፡ በየመንገዱ ከሰው ታወዳጀናለች፤ ከተወዳጀናቸው ታለያየናለች፡፡ እኔም በሕይወቴ ጎዳና በገጠመኝ የእስር ሕይወቴ ካፈራኋቸው ወዳጆቼ ዘላለም ወርቅአገኘሁ አንዱ ነው፡፡ ሁሌ ‹‹ለምን ሳንታሰር አልተዋወቅንም?›› እንባባላለን፡፡ ቀድሞ መተዋወቁ የተለየ ነገር ይፈጥር ይመስል፡፡

Drawing of De Birhan’s co-blogger Zelalem Workagegnehu by Melody Sundberg

Drawing of De Birhan’s co-blogger Zelalem Workagegnehu by Melody Sundberg

ዘላለም ወርቅአገኘሁ በፖሊስ ቁጥጥር ሥር የዋለው ሐምሌ 1፣ 2006 ነበር፡፡ ልክ ከእኛ ውስጥ (ከአቤል በቀር) ወንዶቹ ሁሉ ‹‹ሳይቤሪያ›› ከሚባለው ቀዝቃዛ የምድር ክፍል ወጥተን ‹‹ሸራተን›› ወደሚባለው አንፃራዊ ምቹ ክፍል የተዘዋወርን ዕለት ማለት ነው፡፡ እኛ ወደ‹‹ሸራተን›› የተዛወርነው ለካስ እሱን ጨምሮ ለነሀብታሙ አያሌው፣ አብርሃ ደስታ፣ የሺዋስ አሰፋ፣ ዳንኤል ሺበሺ፣ እንዲሁም ለነባሕሩ፣ ዮናታን፣ አብርሃም እና ሌሎችም ቦታ መልቀቅ ስላለብን ነበር፡፡ አንድም እንዳንቀላቀል፣ አንድም ምሥጢር እንዳንለዋወጥ መሆኑ ነው፡፡ ዘላለም ወርቅአገኘሁ የገባው፣ የኛው ዘላለም ክብረት ወደነበረበት 5 ቁጥር ነበር፡፡ እዚያ ግን ብዙ አልቆየም፡፡ ከዚያ ክፍል ወጥቶ ጭራሹኑ መብራት ወደሌለው እና ከአንድ ሰው በላይ በማያሳድረው ጭለማ ክፍል (ስምንት ቁጥር ) ውስጥ ገብቷል፡፡ ስምንት ቁጥር ውስጥ 41 ቀናት ቆይቷል፡፡

በጨለማ ቤት 24 ሰዓት፣ ለብቻ መቆየት ምን ያክል ከባድ እንደሆነ መገመት ይከብዳል፡፡ ለተወሰኑ ቀናት ከአብርሃ ደስታ ጋር ተጎራብተዋል፡፡ ከዚያ በፊት ባይተዋወቁም (ዘላለም በሥም ያውቀው ነበር) ግድግዳ እየደበደቡ ይነጋገሩና ማፅናኛ ቃላትም ይለዋወጡ እንደነበር ሁለቱም ነግረውኛል፡፡ ዘላለም ከታሰረ ዓመት ሲሞላው ‹‹በእስር ቆይታዬ የተረዳሁት የ24 ሰዓትን ርዝመት፣ የዓመትን እጥረት ነው›› አለኝ፡፡ ‹እንዴት?› አልኩት፤ ‹‹ስምንት ቁጥር እያለሁ 24 ሰዓት ማለት ፈፅሞ የማያልቅ ረዥም የጊዜ ዓይነት ነው፡፡ ዓመት ደግሞ በእስር ዓይን መለስ ብለህ ስትመለከተው በጣም አጭር ነው፡፡ አሁን ሳስበው የገባኝ የሁለቱ አያዎ (paradox) ነው›› አለኝ፡፡ እውነቱን ነው፡፡ ኔልሰን ማንዴላ ‹‹በእስር ቤት አንዱ ቀን ከሌላኛው ቀን፣ አንዱ ሳምንት ከቀጣዩ ሳምንት፣ ወሩ ከሚቀጥለው ወር ጋር አንድ ዓይነት ናቸው›› ብለው ጽፈዋል፡፡ እውነት ነው፤ ስለዚህ መለስ ብለው ሲመለከቱት ዓመቱ በጣም አጭር ይመስላል፡፡ ዘላለም የተረዳው ያንኑ ነው፤ የጨለማ ቤቷን ተሞክሮ የገለፀልኝ ደግሞ እኔ ልገልፀው ስቸገር የነበረውን ነው፡፡

ዘላለም ወርቅአገኘሁ ካየኋቸው ክሶች ሁሉ የተንዛዛ ክስ ነው የተመሠረተበት፡፡ ክሱ ብቻውን ዘጠኝ ገጽ ነው፡፡ ፌስቡክ ላይ ያደረገው ቻት፤ ቤቱ የተገኙ የትምህርት እና ሌሎችም ጽሑፎች በሙሉ ክሱ ውስጥ ተተንትነዋል፡፡ ማስረጃ ተብለው ተያይዘዋል፡፡ ከተያያዙበት የሰነድ ማስረጃዎች መካከል ጥቂቶቹን ለትዝብታችሁ ያክል ልንገራችሁ፡፡

አንድ ገጽ ሙሉ በእስኪርቢቶ የተጻፈ ጽሑፍ ነው፤ እንዲህ ይነበባል፣
“If Blogging is a Crime,
then I am a Blogger too.
Free Zone9 Bloggers”

እንዳየሁት በጣም ነበር የደነገጥኩት፡፡ ብዙ ሰዎች በእጃቸው ‹‹መጦመር ወንጀል ከሆነ እኔም ጦማሪ ነኝ፤ የዞን ዘጠኝ ጦማሪያን ይፈቱ›› የሚል ጽሑፍ ይዘው ፎቶ እየተነሱ ማኅበራዊ ሚዲያ ላይ እየለጠፉ እንደነበር ሰምቻለሁ፡፡ ነገር ግን የሽብር ክስ ማስረጃ ሰነድ ሆኖ ይመጣል ብዬ ግን ጠርጥሬ አላውቅም፡፡ ኢሕአዴግ ብዙ ጊዜ ያስገርመኛል (surprise ያደርገኛል)፡፡ በዚህም አስገረመኝ ከማለት ውጪ ቋንቋ የለኝም፡፡

ሌላም በጣም አስገራሚ ሰነድ ‹‹የሠራኸውን ወንጀል›› ያስረዳል ተብሎ ቀርቦበታል፡፡ ሰነዱ አንዳንዶች እንደሚሉት ‹‹ለኢሕአዴግ ብሉይ ኪዳኑ ነው››፡፡ ሰነዱ “On the Questions of Nationalities in Ethiopia” ይላል፡፡ የብሔር ጥያቄን በወረቀት ደረጃ ለመጀመሪያ ጊዜ አቀንቅኗል የሚባልለት የዋለልኝ መኮንን መጣጥፍ ነው፡፡ ታዲያ የዚህ መጣጥፍ ገጽ ዘላለም ወርቅአገኘሁ ክስ ላይ ማስረጃ ሰነድ ተብሎ ተያይዟል፡፡ ይህንን ሰነድ ምን ብለው ያስተባብሉታል?

እነዚህም ብቻ አይደሉም፡፡ ዘላለም በታሰረበት ወቅት በፐብሊክ አድሚኒስትሬሽን ማስተርሱን በአዲስ አበባ ዩንቨርስቲ እያጠና ነበር፡፡ ታዲያ በወቅቱ ያገላብጣቸው የነበሩ ጥናቶችም ማስረጃ ተብለው ከክሱ ጋር ተያይዘው ቀርበውበታል፡፡ ለምሳሌ የሚከቱሉት ርዕሶች ያሏቸው ጽሑፎች አሉ፤ “Academic freedom” (የትምህርት/ማስተማር ነጻነት)፣ “University for Society” (ዩንቨርስቲ ለማኅበረሰብ)፣ እና “Social Service” (ማኅበራዊ አገልግሎት)፡፡ እንግዲህ እነዚህ በይፋ የሚታወቁ ትምህርት ነክ የሆኑ አጀንዳዎችን የሚታወቁ ጥናቶችን ማስረጃ ብሎ የሽብር ክስ ላይ ማያያዝ አንድም የከሳሾቹን አላዋቂነት ያሳብቃል፡፡ ያውቃሉ ቢባል እንኳ እያወቁ አጥፊነታቸውን ይናገራል፡፡ በተጨማሪም፣ የኔልሰን ማንዴላ ‘Long Walk To Freedom’ የተሰኘውና ከዋናው እትም አጥሮ የተጻፈው መጽሐፍ ገጽ 25 ላይ የሰፈረው፣ ኔልሰን ማንዴላ ‹የሕንድ ብሔራዊ ኮንግረስ›፣ ፓርቲያቸው ‹የአፍሪካ ብሔራዊ ኮንግረስ› ለሚያደርገው ትግል አርኣያ እንደሆነው የሚያትቱበት ጽሑፋቸው ዘላለም ላይ ማስረጃ ተብሎ ተጠቅሶበታል፡፡

ዘላለም በዐቃቤ ሕግ ምስክር ሳይቀር የተነገረበት አንዱ ‹‹በሽብር ተፈርዶበት ውጪ አገር ከሚኖር የግንቦት 7 አመራር ገንዘብ ተልኮለታል›› የሚለው አንዱ ሲሆን፣ ይህንኑ ያስረዳል ተብሎ የተያያዘው ሰነድ ግን የሚያስረዳው ሌላ ነገር ነው፡፡ ሰነዱ የሚያስረዳው ተድላ ደስታ የተባለ ሰው ሦስት መቶ ዶላር እንደላከለት ነው፡፡ ተድላ ደስታ የ‹ደ ብርሃን› ጦማር ጸሐፊ ሲሆን፣ የግንቦት 7 አመራር ቀርቶ አባል ስለመሆኑ ምንም መረጃ ያልቀረበ ከመሆኑም በላይ ‹‹የተፈረደበት›› የሚለው ገሀድ ውሸት ነው፡፡

እንዲህ እና መሰል ክሶችን ታቅፎ የቆየው ዘላለም ነሐሴ 14/2007 ቀድሞ የተከፈተበት አንቀጽ 4 (ሲያንስ 15 ዓመት፣ ሲበዛ ሞት የሚያስቀጣ) ተቀይሮለት በአባልነት ብቻ፣ ማለትም 7/1 (ቢበዛ 10 ዓመት የሚያስቀጣ) አንቀጽ ተደርጎለት እንዲከላከል ተወስኖበታል፡፡ የዛኑ ዕለት በእሱ መዝገብ የተከሰሱት አራቱ የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች እና አብርሃም ሰለሞንም ‹‹ነጻ›› ተብለው ነበር፡፡ ይሁን እንጂ ዐቃቤ ሕግ ይግባኝ በማለቱና የፍቺ እግድም ከጠቅላይ ፍ/ቤት በማሳዘዙ እስከዛሬ አልተፈቱም፡፡ ሌሎቹ የዘላለም ጓደኞች ባሕሩ እና ዮናታንም ቀድሞ በተከፈተባቸው አንቀጽ 7/1 እንዲከላከሉ ተበይኖባቸዋል፡፡ የዘላለም ጓደኞች የተያዙት ከዘላለም ጋር በመሆን ወደውጭ አገር በመጓዝ የኢንተርኔት ደኅንነት ሥልጠና ሊወስዱ በተለዋወጡት ኢሜይል ሳቢያ እንደሆነ ይገመታል፡፡ ሥልጠናውን እያመቻቸላቸው የነበረው በስደት ላይ የሚገኘው ጋዜጠኛ አርጋው አሽኔ ሲሆን፣ አርጋው በክሱ መዝገብ ላይ ‹‹የግንቦት 7 አመራር›› ተብሎ ነው የተጠቀሰው፡፡ አርጋው አሽኔም እንደ ተድላ ደስታ ሁሉ እንኳን የግንቦት 7 አመራር ሊሆን አባል መሆኑንም የሚያስረዳ ማስረጃ የለም፡፡ ዛሬ ዘላለምና አራቱ ፖለቲከኞች በወኅኒ 500ኛ ቀናቸውን ያከብራሉ፡፡ ያከብራሉ ይባላል ወይ ብላችሁ እንዳትጠይቁኝ! ሌሎቹም በዘላለም ሥም በሚጠራው መዝገብ ላይ ያሉ የሕሊና እስረኞች ከሰሞኑ 500 ቀን ይሞላቸዋል፡፡

እኛ ስንያዝ የተረፉ (እና የተሰደዱ) ጓደኞቻችን ሰው ሊረዳላቸው ያልገባቸው ፈተና ውስጥ እንደነበሩ ሲያደርጉ ከነበሩት እና ሲልኩብን ከነበሩ መልዕክቶች ሰምተናል፣ ተረድተናል፡፡ ፈረንጆች ይህ ዓይነቱን ጉዳይ ‘survival’s guilt’ (‹የተራፊዎች የጥፋተኝነት ስሜት› እንበለው?) ይሉታል አሉ፡፡ ከዚያ ደግሞ ድንገት ክሳቸው ተቋርጦ የወጡት አባሪዎቻችን እኛን የከዱን ዓይነት ስሜት ይንፀባረቅባቸው ነበር፤ ይኸው ‹የተራፊዎች የጥፋተኝነት ስሜት› ሳይሆን አይቀርም፡፡ ቀሪዎቹም ተራችን ደረሰና ተንጠባጥበን ስንወጣ እኔ የጓደኞቼን ሕመም በከፊልም ቢሆን የተረዳሁት የመሰለኝ ዘላለምን ተሰናብቼ ስወጣ ነው፡፡

ዘላለም እስሬን ካቀለሉልኝ ሰዎች ውስጥ ዋነኛው ነው፡፡ ውይይታችን፣ ንትርካችን ሁሉ የማይዘነጋ ነበር፡፡ ማታ፣ ማታ መታጠቢያ ክፍሉ ውስጥ ካለች ጠባብ ኮሊደር ውስጥ የባጥ የቆጡን እየቀባጠርን እስከ ሌሊቱ ሰባትና ስምንት ሰዓት የምንቆይበት ጊዜ ነበር፡፡ በተለይ አምስቱ አባሪዎቼ ድንገት የወጡ ጊዜ የነበረውን የሐሳብ ውዥንብር እና የእንቅልፍ መዋዠቅ ከእሱ ጋር በማውራት ነበር ሰውነቴን ያላመድኩት፡፡ በእስር ቤት ቋንቋ ገበታ በጋራ የሚቋደሱ ሰዎች፣ መቅዱስ ነበር የሚባሉት፡፡ ዘላለም መቅዱሴ ብቻ አልነበረም፡፡ ወኅኒ የሰጠኝ ጓደኛዬም ነው፡፡ አሁን እቤቴ ቁጭ ብዬ አስበዋለሁ፡፡ ሳያመሽ መተኛት አይችልበትም፤ በጣም ያመሻል፡፡ ለቆጠራ 12፡30 በራችን ሲንኳኳ ‹ሀንጎቨር› እንዳለበት ሰው ዓይኑ ቅልትልት ብሎ፣ ፎጣ ደርቦ ሲወጣ ይታወሰኛል፡፡ ኳስ ጨዋታ ሲኖር (እኔ ባልወድም) ከጎረምሳው ሁሉ ጋር ሲሟገት ይታየኛል፡፡ ሰው መንከባከብ ይችልበታል፤ ሲንከባከበኝ ትዝ ይለኛል ልበል? አዎ፣ እንደሚንከባከበኝ ስለማውቅ እኔም እቀብጥ ነበር፤ እሱም ሲንከባከበኝ አስገራሚ ነው፡፡

ዘላለም ወርቅአገኘሁ እና ጓደኞቹ (5 ሆነው) የመጪው ሰኞ፣ ሕዳር 13፣ 2008 ራሳቸውን ለመከላከል ከፍተኛው ፍርድ ቤት ይቀርባሉ፡፡ እኔም እንደተመልካች ላያቸው እሄዳለሁ፡፡ አልጨብጣቸውም፡፡ እጄን የማውለበልብላቸው ከሆነ እንኳን ፈራ ተባ እያልኩ ነው፡፡ እኔ ከትልቁ እስር ቤት ሆኜ፣ እነርሱ ደግሞ ከጠቧቧ ሁነው ያዩኛል፡፡ ‹ሁላችንም ነጻ ካልወጣን፣ አንዳችንም ነጻ ወጣን ማለት አይቻልምና!›

መልካም ዕድል ከመመኘት በላይ ምን አቅም አለኝ፡፡ መልካም ዕድል፣ የክፉ ቀን ጓዴ! መልካም ዕድል!

The post ዛሬ 500 ቀናት በእስር የሚሞላው የወኅኒ ጓደኛዬ ትዝታ | በፍቃዱ ዘ ኃይሉ appeared first on Zehabesha Amharic.

ኢ/ር ይልቃል ጌትነት ብሪታኒያ ከኢትዮጵያውያን ጎን እንድትቆም ጥሪ አቀረቡ

$
0
0

• ‹‹የዓለም አቀፉ ማህበረሰብ የፖለቲካ ቁርጠኝነት ማነስ ኢትዮጵያን ከመፍትሄ አካልነት ወደ ችግርነት እያንደረደራት ነው››

• ‹‹በቀጠናው የሚደረገው የእሳት ማጥፋት ፖለቲካ ኢትዮጵያን ወደ አለመረጋጋት እየመራ ነው›› ኢ/ር ይልቃል ጌትነት

 

Yilikal

በነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተር

የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር ኢ/ር ይልቃል ጌትነት በኢትዮጵያና በአፍሪካ ህብረት የብሪታኒያ አምባሳደር የሆኑትና የስራ ዘመናቸውን አጠናቀው የሚመለሱት አምባሳደር ግሪጎሪ ጋር ህዳር 9/2008 ዓ.ም ባደረጉት ውይይት የኢትዮጵያ የረዥም ጊዜ ወዳጅ የሆነችው ብሪታኒያ በዚህ አስቸጋሪ ወቅት ከኢትዮጵያውያን ጎን እንድትቆም ጥሪያቸውን አቅርበዋል፡፡ በሰማያዊ ፓርቲ ፅ/ቤት ከሊቀመንበሩ ጋር ለአንድ ሰዓት ያህል ውይይት ያደረጉት የብሪታኒያ አምባሳደር በወቅታዊ ሀገራዊና ቀጠናዊ ጉዳዮች ላይ በስፋት ተነጋግረዋል፡፡

ከ2007 ዓ.ም ምርጫ በኋላ ያለውን የኢትዮጵያን ሁኔታ በስፋት ያስረዱት ኢ/ር ይልቃል ጌትነት የወጣቱ ስራ አጥነት፣ የፖለቲካው አፈና፣ ሙስና፣ የኑሮ ውድነቱና ሌሎችም ችግሮች በመቀጠላቸውንና በአሁኑ ወቅት የተከሰተው ርሃብም የእነዚህ ሁሉ ችግሮች ድምር መሆኑን አስረድተዋል፡፡ በተጨማሪም ዜጎች ከቀያቸው ያለ አግባብ እንደሚፈናቀሉ፣ ይህንንም ሲክድ የነበረው መንግስት የተወሰኑትን መክሰሱን በጋምቤላ ክልል ዜጎችን ያፈናቀሉ ከፍተኛ ባለስልጣናትን ላይ ራሱ መንግስት የመሰረተውን የክስ መዝገብ አስደግፈው ለአምባሳደሩ አስረድተዋል፡፡

ኢትዮጵያ ይህ ሁሉ ችግር ውስጥ እያለች ዓለም አቀፍ ማህበረሰቡ በቀጠናው ያለውን ችግር ለማብረድ ሲባል ለአጭር ጊዜ ጥቅም ከአገዛዙ ጋር በፈጠሩት ግንኙነት፣ ለኢትዮጵያ ችግር የበኩላቸውን ምላሽ ለመስጠት ፈቃደኛ አለመሆናቸውን ሊቀመንበሩ ወቀሳ አቅርበዋል፡፡
በአፍሪካ ቀንድ በሚወሰደው የእሳት ማጥፋት እርምጃም የአጭር ጊዜ ጥቅምን እንጅ የረዥም ጊዜ ስትራቴጅካዊ ግንኙነትን ያላገናዘበና ኢትዮጵያንም ወደ አለመረጋጋት እየመራ እንደሆነ ለአምባሳደሩ ገልፀውላቸዋል፡፡ በአጭር ጊዜ መፍትሄ ላይ ትኩረት እያደረገ የሚገኘው የዓለም አቀፉ ማህበረሰብ የፖለቲካ ቁርጠኝነት ማነስ ኢትዮጵያን ከመፍትሄ አካልነት ወደ ችግርነት እያንደረደራት እንደሆነም አብራርተዋል፡፡ ብሪታኒያ የኢትዮጵያ የረዥም ጊዜ ወዳጅ በመሆኗም በዚህ አስቸጋሪ ወቅት ከአገዛዙ ይልቅ ከኢትዮጵያውያን ጎን እንድትቆምም የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር ጥሪያቸውን አቅርበዋል፡፡

The post ኢ/ር ይልቃል ጌትነት ብሪታኒያ ከኢትዮጵያውያን ጎን እንድትቆም ጥሪ አቀረቡ appeared first on Zehabesha Amharic.

የቤኒሻንጉል ህዝቦች ነጻነት ንቅናቄ 3 አባላቱን ማባረሩን አስታወቀ

$
0
0

ብስሚላሂ-ኣልረህማን-ኣልረሂም
በጠላት ተደልለው የህዝቦችን ፍትሃዊ ትግል ለማደናቀፍ የሚንቀሳቀሱ
ሃዲያን ፍትሃዊ ትግሉን ሊቀለብሱ ኣይችሉም!

ከቤኒሻንጉል ህዝቦች ነጻነት ንቅናቄ የተሰጠ መግለጫ

የቤኒሻንጉል ህዝቦች ነጻነት ንቅናቄ ባለፉት ረጅም ዓመታት ህዝቦቻችን ላይ ሲደርስ የነበረውንና ኣሁንም ስልጣኑን በያዘው ኣምባገነኑ የወያኔ መንግስት እየደረስ ያለውን ጭቆናና የመብት ጥሰት በማስቆም እኩልነት፣ ፍትህ፣ ዱሞክራሲና ነጻነትን በማረጋገጥ ህዝቦች በሃገራቸው ላይ የነጻነትና የሰላም ኣየር እንዱተነፍሱ ለማድረግ ትግል በማካሄድ ላይ ይገኛል ። እያካሄድን ያለነው ትግልም ከጊዜ ወደ ጊዜ ህዝባዊ ፍቅርና ድጋፍ እያገኘና እያደገ ሲሆን በዚህም በርካታ የቤኒሻንጉል ተወላጆች ወደ ድርጅታችን በመቀላቀል ድርጅቱ የሰጣቸውን ግዳታ በመወጣት ላይ ናቸው። ሃገር ቤት ያለው ወገናችን ወደ ሰራዊታችን በመቀላቀል የትጥቅ ትግሉን ከማካሄድና በተለያየ መልኩ እየደገፈ እንዲለው ሁሉ የኢትዮጵያ መንግስትን ጭቆና በመሸሽ በተለያዩ የውጪ ሃገራት የሚገኙ የቤኒሻንጉል ተወላጆችም ወደ ትግላችን በመቀላቀል ከድርጅታችን በሚሰጣቸው መመሪያ መሰረት ትግለን በማፋጠን ላይ ይገኛለ።

Zehabesha News

በሌላ በኩል ደግሞ ቀደም ሲል በድርጅታችን ኣባልነት ታቅፈው ሲንቀሳቀሱ የነበሩ ኋላ ላይ ግን በጠላት ፕሮፓጋንዲና መደለያ ተታልለው የህዝቦችን ትግል ለማኮላሸት የሚንቀሳቀሱ ኣንዲንድ ግለሰቦች የወያኔን ተልዕኮ ለማሳካት ሲሰሩ ታይተዋሌ። ድርጅታችን እነዚህ ኣባላት ከስህተት መንገዲቸው ተመልሰው ትላንት መስዋዕትነት የተከፈሉበትንና ኣሁንም ውድ የህይወት ዋጋ እንዱሁም የተለያዩ መስዋዕትነቶች እየተከፈሉበት ባለው የህዝቦች ትግል የዜግነት ድርሻቸውን እንዱወጡ ሲያደርግ ነበር። ሆኖም ግን እንዲንድ ግለሰቦች ከዚህ የወያኔን ስውር ዓላማ ካነገበ ድርጊታቸው ለታቀቡ ባለመቻላቸው ድርጅታችን የቤኒሻንጉል ህዝቦች ነጻነት ንቅናቄ ተገቢውን እርምጃ ለመውሰድ ተገድዷል።

በዚሁ መሰረት በየመን የወያኔ ኣምባሳደር የነበረው ዩሱፍ ሃሚድና ልጁ ኻሊድ ዩሱፍ እንዱሁም ኢብራሂም ዩሱፍ የተባሉ ግለሰቦች እስከ 2013ዓም ድረስ የድርጅታችን ኣባል የነበሩና በድርጅቱ ዓላማና መመሪያ ሲንቀሳቀሱ እንደነበር ይታወሳል። ሆኖም ግን እነዚህ ግለሰቦች ከቅርብ ጊዜ ወዱህ የድርጅታችን፡ የቤኒሻንጉል ህዝቦች ነጻነት ንቅናቄን ዓላማ የሚጻረር ድርጊት ሲፈጽሙ የታዩ ሲሆን ከዚህ እኩይ ተግባራቸው ታቅበው የድርጅታችን ህግና ድንብ በሚፈቅደው መሰረት እንዱንቀሳቀሱ ምክርና ማስጠንቀቂያ ቢሰጣቸውም ሊታቀቡ ኣልቻሉም። እንዱያውም ድርጅታችን ፍትሃዊ ትግሉን በኣፋጣኝ ከግቡ ለማድረስና ህዝቦቻችንን ከጭቆና ለማላቀቅ በተለያየ መልኩ እያደረገ ያለውን እንቅስቃሴ ለማደናቀፍና የጠላትን ዓላማ ከግቡ ለማድረስ በገሃድ በመስራት ላይ ናቸው።

በመሆኑም ድርጅቻችን እነዚህ የህዝቦቻችን ቀንደኛ ጠላት ከሆነው የወያኔ መንግስት ጋር በመመሳጠር ትግላችንን ለማደናቀፍና በጀግኖቻችን መስዋዕትነት ያገኘነውን ድል ለመቀልበስ የሚሯሯጡት ሶስቱ ግለሰቦች ላይ የመጨረሻ እርምጃ በመውሰድ ዛሬ ህዳር 18 ቀን 2015 ዓም ከደርጅቱ ኣባልነት ሙሉ ለሙሉ ያባረረ መሆኑን ለመግለጽ ይወዳል። ከዚሁ ጋር በማከልም የድርጅታችን ኣባላትና ደጋፊዎች እንዱሁም ህዝባችንና ኣጋሮቻችን እነዚህ ግለሰቦች በየትኛውም እንቅስቃሴያቸውና ድርጊታቸው ድርጅታችንን የማይወክሉ፡ የጠላት ተላላኪ ከሃድያን መሆናቸውን እንዱገነዘቡ እንፈልጋለን።

በመጨረሻም የጠላትን ድብቅ ተልዕኮ ይዘው በተለያዩ ወጪ ሃገራት በሚኖሩ የሃገራችን ዜጎች ዘንድ በመሄድ ወያኔያዊ መርዝ ለማሰራጨትና የትግል እንቅስቃሴያችንን ለማደናቀፍ ለሚጥሩ ማናቸውም የጠላት ተላላኪ ሃዱያን ድርጊታቸው ፍትሃዊ ትግሉን እንደማይቀለብስና ከታሪክ ተጠያቂነት የማያወጣቸው መሆኑን እያሳሰበ፡ ህዝቦች እያካሄዱት ያለው ፍትሃዊ ትግል ደግሞ በጠላትና በከሃዲያን መደለያና መሰረተ-ቢስ ወሬ የማይደናቀፍ መሆኑንም ቤ.ህ.ነ.ን በጥብቅ ያስገነዝባል።

የቤኒሻንጉል ህዝቦች ነጻነት ንቅናቄ

The post የቤኒሻንጉል ህዝቦች ነጻነት ንቅናቄ 3 አባላቱን ማባረሩን አስታወቀ appeared first on Zehabesha Amharic.

ችጋር በሰው ዘር ላይ የሚፈጸም ወንጀል ነው –ያሬድ ኃይለማርያም ከብራስልስ  

$
0
0

 

Yared

Yared

ህዳር 10 ቀን 2008

አለም እጅግ በሰለጠነበት በዚህ ክፍለ ዘመን፣ የሰው ልጅ በእውቀትና በቴክኖሎጂም በመጠቀበት ወቅት በሚሊዮኖች የሚገመቱ ሰዎች የሚላስ የሚቀመስ አጥተው፣ ሰማይና ምድሩ ተዳፍኖባቸው ከሞት አፋፍ የሚደርሱበትና ከፊሉም የሚሞቱበት አገርና ስፍራ ቢኖር እንደ ኢትዮጵያ ያሉ ማሕበራዊ ፍትሕ የተጓደለባቸው፣ ሙሰኝነት መረን በለቀቀ መልኩ በተንሰራፋባቸው፣ ፍጹም የሆነ አንባገነናዊ ሰርዓት በሰፈነባቸው እና የህግ የበላይነት ባልተረጋገጠበት አገሮች ወይም እንደ ሶማሊያ ባሉ መንግስት አልባ ሆነው ለረዥም አመታት በትርምስና እልቂት ውስጥ በቆዩ ጥቂት አገሮች ብቻ ነው፡፡ ኢትዮጵያ ውስጥ የሚከሰተውን ችጋር በተመለከተ እረዘም ላለ ጊዜ ጥናት ያካሄዱትን ፕ/ር መስፍን ወልደማሪያምን ጨምሮ በርካታ አለም አቀፍ ተመራማሪዎች በጥናቶቻቸው እንዳረጋገጡት የ‘ችጋር’ ምንጩ የተፈጥሮ አየር ንብረት መዛባት ወይም የእዝጌር ቁጣ ሳይሆን ብልሹ የፖለቲካ አስተዳደርና የተሳሳተ የመንግሥት ፖሊሲ ወይም የአፈጻጸም ችግር የሚያስከትለው አደጋ ነው፡፡ ከአንድ መጥፎ ሥርዓት ወደ ባሰ መጥፎ ሥርዓት ስትንከባለል የመጣችው አገራችንም ከ1958 ዓ.ም ወዲህ ባሉት ጊዜያቶች ውስጥ ለበርካታ ጊዜያት ችጋር አንጃቦባታል፡፡ ቁጥራቸው ቀላል ግምት የማይሰጣቸውን ድሃ ልጆቿንም እንደ ጩልፊት አሞራ ነጥቋታል፡፡

ይህ አንባገነንና አፋኝ ሥርዓትን እንደ ጥላ የሚከተለው የችጋር አዙሪት ዛሬም አገሪቱ በልማት ገስግሳለች እየተባለ ሌት ተቀን በአለም አቀፍ ሚዲያዎች ሳይቀር በሚዘፈንበት ወቅት የአሥራ አምስት ሚሊዮን ድሃ ልጆቿን ሕይወት ሊቀጥፍ እንደ ጩልፊት አሞራ እያንጃበበ መሆኑን ከአገዛዙ ልሳን ጭምር እየሰማን ነው፡፡ የአገዛዝ ስርዓቱ ለዚህ አደጋ አራሱን ተጠያቂ ላለማድረግ ሁለት ዋና ምክንያቶችን እየደረደረ ነው፡፡ አንድም ችግሩ የተከሰተው በአለም አቀፍ ደረጃ በተከሰተው የአየር መዛባት መሆኑን እና በሁለተኛ ደረጃም ችግሩ የተባባሰው አገሪቱ በልማት ጎዳና ላይ ብትሆንም ገና በምግብ እራሱዋን ያልቻለች ደሃ አገር ስለሆነች ነው የሚል ነው፡፡ የመጀመሪያውን ምክንያት ድርቅን ከማስከተል ያለፈ የችጋር አደጋን ሊያመጣ እንደማይችልና ድርቅ ወደ ችጋር የሚለወጠው በምሁራኖቹ ጥናት እንደተረጋገጠው የብልሹ ሥርዓት ውጤት ስለሆነ እሱ ላይ በዙ ማለት አይጠበቅብኝም፡፡ ሁለተኛውን ምክንያት የተመለከትን እንደሆነ በእርግጥም ኢትዮጵያ ድሃ ልጆቿን በችጋር ከሚደርስ የሞት አደጋ ለመታደግ በሚያስቸግር ደረጃ ላይ የምትገኝ ደሃ አገር ነች ወይ የሚል ጥያቄን ያጭራል፡፡

በአገሪቱ የተላያዩ ክፍሎች የችጋር ምልክት መታየት የጀመረው ከአመት በፊት ነው፡፡ በተለይም በአፋርና በሶማሌ ክልል አካባቢ እንስሳቶች መሞት የጀመሩት፣ በምግብና በመጠጥ ውሃ እጦት ሰዎች ከቅያቸው መሰደድ የጀመሩት ከወራቶች በፊት ነው፡፡ ጉዳዩም በተለያዩ የመገናኛ በዙሃን ሲዘገብ ቆይቷል፡፡ እንደሚታወቀው እነዚህ አካባቢዎች በተለይም በሶማሌ ክልል ኦጋዴን አካባቢ ለረዥም ጊዜ የበጎ አድራጎት ድርጅቶች ጭምር ወደ ክልሉ እንዳይገቡና እርዳታ እንዳያደርጉ የአገዛዝ ሥርአቱ የከለከለ በመሆኑ እየደረሰ ያለውን የጉዳት መጠን እንኳን በትክክል ለማወቅ አልተቻለም፡፡ የአገዛዝ ሥርዓቱም ችግሩን በማጤን አፋጣኝ እርምጃዎችን ከመውሰድ ይልቅ የሥልጣን ዘመኑን ለማደስ ባካሄደው የይስሙላ ምርጫና የተገኘውን መቶ ፐርሰንት ድል በማጣጣም ላይ ተጠምዶ ስለነበር በሚሊዮን የሚቆጠሩት ድሆች የሚያሰሙትን የድረሱልን ጥሪ የሚሰማበት ጆሮና የሚያይበት አይን አልነበረውም፡፡ መንግስት ከመደበኛ ስራዎች ባሻገር በብዙ ሚሊዮኖች የሚገመት ገንዘብ ከሚያፈስባቸው ጉዳዮች ጥቂቶቹን ብንመለከት አገሩቱ በችጋር እየተጠበሱ የሚረግፉ ልጆቿ ለመታደግ የሚስችለውን አቅሟን ሥርዓቱ በምን ላይ እያዋለው እንደሆነ በግልጽ ያመላክታል፡፡

  • በቅርቡ ሥርዓቱ በአለማችን የተለያዩ ከፍሎች ተበትነው ጥቂት ቅሪት ያካበቱ በውጭ የሚኖሩ ኢትዮጵያዊና ትውልደ ኢትዮጵያዊያንን ድል ያለ ድግስ ደግሶና 40 ፐርሰንት የአውሮፕላን ትኬታቸውን ወጪ ሸፍኖ ሲያበላ፣ ሲያጠጣና አገር ሲያስጎበኝ ቆይቷል፡፡ ለዚህም በሚሊዮኖች የሚገመት የአገሪቷን ሃብት እንዳፈሰሰ በሚቆጣጠራቸው መገናኛ ብዙሃን አርድቶናል፡፡
  • ባለፉት ሁለትና ሶሰት አመታተ ውስጥ ሥርዓቱ በውጭ የሚገኙ ኢትዮጵያዊያንን የፖለቲካ ድጋፍ ለማግኘት ሲል በየኤምባሲው እጅግ ከፍተኛ ገንዘብ አፍሶ ድል ያለ ድግስ በመደገስ ከአገር ውጭ በተደላደለ ኑሮ ውስጥ የሚገኙ ኢትዮጵያዊያንን ሲያበላና ሲያጠጣ ከርሟል፡፡ እኔ በምኖርባት አገር የሚገኘው ኤምባሲ እንኳን በተደጋጋሚ ጊዜያት ከ300-400 የሚገመቱ የቤልጂየምና የጎረቤት አገር ነዋሪዎችን እየጋበዘ ከኢትዮጵያ ድረስ አስጭኖ ያስመጣውን ምግብና መጠጥ በከፍተኛ ገንዘብ በተከራያቸው ውድ አዳራሾች ሲያበላና ሲያጠጣ ታዝበናለ፡፡ በችጋር ከሚረግፉት ሚሊዮኖች ጉሮሮ እየነጠቀ በድሎት ከሚኖሩ ጥቂቶች ጋር ቢራና ውስኪ የሚያራጭበት ምክንያት ግልጽ ነው፡፡
  • ከአነስተኛ ሹማምነት አንስቶ እሰከ ከፍተኛ ደረጃ ያሉ የአገዛዙ ባለሥልጣናትና ካድሬዎች ከገቡበት የሙስና አዘቅት ባሻገር ለሥርዓቱ ያላቸውን ታማኝነት ይዘው እንዲቆይ ሲባል ለነሱና ለቤተሰቦቻቸው ምቾት የሚባክነው ገንዘብ ቀላል ግምት የሚሰጠው አይደለም፡፡ አፈ-ጉዔው አቶ አባዱላ ባለፈው አመት በተወካዮች ምክር ቤት የአፍ ወለምታ ይሁን ከልብ አስበውበት “እኔን ጨምሮ እያንዳንዱ የመንግሥት ባለሥልጣናት ከአንድም ሁለት የሰባት ሚሊዮን ብር እና ከዛ በላይ የሚያወጡ መኪኖችን ለራሳቸውና ለቤተሰባቸው መገልገያ በመንግሥት ባጀት ማዘዛቸውን ማቆም አለባቸው” ሲሉ የተናገሩትን መጥቀስ ይቻላል፡፡ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ዜጎች በርሃብ፣ በውሃ ጥም፣ በሕክምና እጦትና በሌሎች መሰረታዊ አቅርቦቶች ችግር በሚለበለቡበት አገር ባለሥልጣናቱ አይን ካወጣ ዝርፊያና ንጥቂያ አልፈው የድሎት በጀት አስበጅተው የአገር ሃብት ሲያባክኑ እየታየ ነው፡፡
  • የገዢው ፓርቲና አጋሮቹ በየጊዜው እየተነሱ የሚያከብሩዋቸው ድርጅታዊ በዓላት በሚሊዮን የሚገመት ገንዘብ የሚፈስባቸው ናቸው፡፡ በቅርቡ በጅጅጋ የተካሄደውን የወያኔን የድል በዓል አከባበር ማየት በቂ ነው፡፡ የክልሉ ሕዝብ በርሃብና በውሃ ጥም እየተሰቃየና እርዳታ እየተማጸነ ባለበት ወቅት የአገዛዝ ሥርዓቱ በመላ አገሪቱ ያሉትን ካድሬዎች ጅጅጋ ላይ ሰብስቦ ለአንድ ሳምንት ጉሮ-ወሸባዮ ይል ነበር፡፡
  • በየጊዜው እየተሰነጣተቀ የሚገጥመውን የገዢውን ፓርቲ የፖለቲካ ገጽታ ለማሳመርና ያገዛዙን ዘመን ለማራዘም የሚባክነውም ገንዘብ እጅግ ከፍተኛ ነው፡፡ በባለሥልጣናትና በካድሬዎቻቸው በስብሰባና የውጭ ጉዞዎች የሚባክነውን ከፍተኛ ገንዘብ እንተወውና ሥርዓቱ የተለየ የፖለቲካ አመለካከት ያላቸውን ፖለቲከኞች፣ ስርዓቱን የሚተቹ ጋዜጠኞችንና የማህበራዊ ድረ-ገጾችን፣ የተቃዋሚና ገለልተኛ ሚዲያዎችን ለማፈንና ለመሰለል የሚያወጣውም ገንዘብ በሚሊዮን ዶላር የሚገመት እንደሆነ በቅርቡ በጣሊያንና በጀርመን ከሚገኙ በኢንተርኔት ጠለፋና ሥለላ ሥራዎች ላይ ከተሰማሩ ደረጅቶች ጋር የነበረው ግንኙነት ጥሩ ማሳያዎች ናቸው፡፡ በሚሊዮን የሚቆጠር ሕዝብ በሚራብበት አገር ከነሱ ጉሮሮ ነጥቆ በሚሊዮኖች የሚገመት ዶላ ወጪ አድርጎ አንድ ሺ የማይሞሉ ተቃዋሚዎቹንና ተቺዎቹን መሰለያ የሚሆኑ የኮምፒውተር ፕሮግራሞችን የሚገዛ ድርጅተ ነው፡፡

እነዚህን እና ሌሎች የአገዛዝ ሥርዓቱ በአገርና በሕዝብ ሃብትና ገንዘብ ላይ የሚፈጽማቸውን ብክነቶች እያሰብን ከፍለፊታችን የተጋረጠውን የችጋር አደጋ ስንመለከት ስርዓቱ ከጥይት፣ ከእስር፣ ከስደትና ከልመና የተረፉትን ድሃ የሃገሪቱን ዜጎች ለችጋር አሳልፎ የሰጣቸው መሆኑን ነው የምንመለከተው፡፡ ከላይ በተጠቀሱት መንገዶችና በተመሳሳይ ሁኔታዎች ከሚባክነው ከፍተኛ ገንዘብና በተለያዩ ጊዜያት ከአገር የሚሸሸውን የገንዘብ መጠን ስንመለከት ኢትዮጵያ ደሃ ሳትሆን የተፈጥሮ ሃብቷንና ገንዘቧን በአግባቡ የሚያስተዳድርላት ሰውና የፖለቲካ ሥርዓት ነው ያጣችው፡፡

ለአገርና ለወገን የሚቆረቆር ጤናማ የፖለቲካ አመራር ባለበት ሃገር በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ሰዎች የምግብ ዋስትና በማጣት ከሞት ደጃፍ አይደርሱም፡፡ ህሊናቸውን ያልሳቱ፣ በሕዝብ ገንዘብ አእምሮዋቸው ያልናወዘና ስብዕና የሚሰማቸው የፖለቲካ አመራሮች ባሉበት አገር ሹመኞች ከነልጆቻቸው በሚሊዮን ዶላር በሚገዙ መኪኖች እየተንፈላሰሱና በተንጣለሉ ቪላዎች እየተመናሹ የድሃ ልጆች ቁራሽ ዳቦ የሚታደጋቸው አጥተው በየመንገዱ ጠኔ አይጥላቸውም፡፡ ይህ የሚሆነው በተቃወሰ የፖለቲካ፣ የማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ሥርዓት ውስጥ ብቻ ነው፡፡ አንድ የመንግሥት ሹመኛ ወይም ወታደራዊ ባለስልጣን ወይም የሥርዓቱ ደጋፊ የሆነ ሰው ባጭር አመታት ውስጥ ከመንግሥት ደሞዝተኝነት ተነስቶ ምንጩ ባልታወቀ ሁኔታ ሚሊዮነር ሲሆንና የከፍተኛ ሃብት ባለቤት ሊሆን የሚችለው መረን የለቀቀ ሙስና በተንሰራፋበት ሃገር ብቻ ነው፡፡ እነዚህ ሰዎች መንግስት የሚከፍላቸውን የወር ደሞዝ አንድም ሳንቲም ሳይቀነስለት ለመቶ አመታት እንኳን ሙሉውን በባንክ እንዲቀመጥ ቢደረግ ስሌቱ ባንድ ጀምበር ዛሬ ላይ ያፈሩትነ ሃብት የእሩብ እሩቡ እንኳ እንዲኖራቸው የሚያስችል አይደለም፡፡ ከትቢያ ተነስተው የግዙፍ ህንጻዎችና ኩባንያዎች ባለቤት የሚሆኑት ከሕዝበ ጉሮሮ በነጠቁት ገንዘብ ካልሆነ በቀር ከየት አምጥተው እንደሆነ ሕዝብ የማወቅና የመጠየቅ መብት አለው፡፡

በተባበሩት መንግሥታት የሰብአዊ መብቶች ድንጋጌ አንቀጽ 25(1) እንዲሁም በአለም አቀፉ የኢኮኖሚ፣ ማህበራዊና ባህላዊ መብቶች ድንጋጌ በአንቀጽ 11 ላይ በግልጽ እንደተቀመጠው እያንዳንዱ ሰው እራሱና ቤተሰቡን በተሟላ ጤንነትና ለሰው ልጅ ክብር በሚገባ ሁኔታ የመኖር ዋስትና እንዲረጋገጥለት፣ እንዲሁም በቂ የሆነ ምግብ፣ አልባሳት፣ መጠለያ ቤትና የህክምና ግብአቶችን የማግኘት መብት እንዳለውና መንግስትም እነዚህን መሰረታዊ ነገሮች የማሟላት ግዴታ እንዳለበት ይደነግጋል፡፡ ይህን ግዴታቸውን መወጣት ካልቻሉት ጥቂት የአለማች አገሮች አንዷ ኢትዮጵያ ነች፡፡ ኢትዮጵያ ውስጥ ያለውን የምግብ ዋስትና ማጣትን ተከትሎ ሚሊዮኖችን አደጋ ላይ እስከ መጣል የደረሰውን የችጋር አደጋ የከፋ የሚያደርገው የአገዛዝ ሥርዓቱ አደጋውን ችላ ከማለቱም ባሻገር ለማለባበስ የሚያደርገው አሳፋሪ ጥርት ነው፡፡ የBBC ጋዜጠኛ በNovember 9, 2015 ጥናታዊ ዘገባው (http://www.bbc.com/news/world-africa-34770831 ) ችግሩ በተከሰተባቸው ሥፍራዎች፤ በተለይም ወሎ ውስጥ ቆቦ አካባቢ በመዘዋወር የችጋሩ ተጠቂ የሆኑ ሰዎችን አነጋግሮና በችጋር ልጇን ያጣች አንዲት እናት ጨምሮ ምስክርነታቸውን የሰጡትን ሰዎች የገዢው ፓርቲ ካድሬዎችና ልማታዊ ጋዜጠኞች ቃላቸውን እንዲያስተባብሉና በችጋር የሞተ የለም ብለው እንዲናገሩ አስገድደዋቸዋል፡፡ የሚያሳዝነው እንዲህ ያለውን አስነዋሪና ከጋዜጠኝነት ሥነ-ምግባር በራቀ መልኩ የቪኦኤው የመቀሌ ዘጋቢ ከመቀሌ ቆቦ ድረስ ተጉዞ የአገዛዙን ገበና ለመሸፈን ተመሳሳይ ድርጊት መፈጸሙ ነው፡፡

ይህ እጅግ አሳፋሪና አስነዋሪ ተግባር ከመሆኑማ ባሻገር የተራበን ሰው አልተራብኩም በል፣ በርሃብ ልጇን ያጣችን ድሃ እናት ልጄ በበሽታ ነው የሞተው ብላ እንድትናገር ማስገደድ የሥርዓቱን ብልሹነት በግልጽ ያሳያል፡፡ ለዚች እናት ህመሙ በደርግ ጊዜ የተገደሉባቸውን ልጆቻቸውን አስከሬና ለመውሰድ የጥይቱን ዋጋ እንዲከፍሉ ከተገደዱት እናቶች እኩል ነው፡፡ የእዚች እናት እመም የመንግስት አድራጎት በ1997 ዓ.ም. ምርጫውን ተከትሎ በተቀሰቀሰው ግጭት የትምህርት ቤት ደጃፎቻቸው ላይ በአጋዚ ጦር ግንባራቸውን እየተመቱ የወደቁትን ሕጻናት ባንክ ሊዘርፉ ሲሉ ነው የተገደሉት የሚል የማላገጫ ምክንያት እንደተሰጣቸው እናቶች ነው፡፡

ሥርዓቱና ይህ ጉዳይ በቀጥታ የሚመለከታቸው ባለሥልጣናት በችጋር ለሚሰቃየውና ለሚያልቀው ሕዝብ በታሪክ ተወቃሽ ከመሆን ባለፈ በተለይም በኦጋዴንና በተወሰኑ የአገሪቱ ክፍሎች የሚገኙ አርሶ አደሮችና አርብቶ አደሮች በችጋር እየተጠቁ መሆኑን እየታወቀ ከአመት በላይ ተገቢውን እንዳታ ባለማድረጉና ለጋሽ ድርጅቶችም ሕዝቡን እንዳይታደጉ እቀባ በመጣሉ የተነሳ ለሚደርሰው ሰብአዊና ሌሎች ጉዳቶች ሁሉ በችጋር የሰውን ዘር ሆነ ብሎ አደጋ ላይ በመጣል በሕግ የሚያስጠይቃቸው መሆኑን ከወዲሁ ልብ ሊሉት ይገባል፡፡

 

አስተዋሽ አጥተው ለችጋር ለተጋለጡት ወገኖቻችን እጃችንን እንዘርጋ!

ያሬድ ኃይለማርያም

https://humanrightsinethiopia.wordpress.com/

 

 

 

 

 

 

 

 

 

 

 

 

 

 

The post ችጋር በሰው ዘር ላይ የሚፈጸም ወንጀል ነው – ያሬድ ኃይለማርያም ከብራስልስ   appeared first on Zehabesha Amharic.


Health |‹‹በጭንቀት እየተሰቃየሁ ልሞት ነው፤ መፍትሄውን ጠቁሙኝ››

$
0
0

ስለሁሉም ነገር እጨነቃለሁ፡፡ ትንንሽ ነገሮች እንኳ ያሳስቡኛል፣ ያስጨንቀኛል፣ ያበሳጨኛል፡፡ ለመተኛት አልጋዬ ላይ ስወጣ ከአንዱ ጉዳይ ጭንቀት ወደ ሌላኛው ጉዳይ ጭንቀት ስመላለስ እንቅልፌን አጣለሁ፡፡ አንዳንዴ ስጨነቅ አድሬ ይነጋብኝና ተነስቼ ወደ ስራ እሄዳለሁ፡፡ ከቤተሰቦቼ አንዱ የሆነ ነገር ሲያማክረኝ ‹ባክህ ከጭንቀቴ ላይ ጭንቀት አትጨምርብኝ› ብዬ እጮህባቸዋለሁ፡፡ ሥራ ገብቼ ትኩረቴን መሰብሰብ ያቅተኛል፡፡ የማታ ትምህርት ጀምሬ ጭንቀቴ ሲበዛብኝ አቋረጥኩት፡፡ 

በመጀመሪያው ሴሚስቴር ጥሩ ውጤት አምጥቼ በሁለተኛው ሴሚስተር ሳቋርጠው ያላዘነብኝ ሰው የለም፡፡ መተዌን ሳስበው እጨነቃለሁ፤ እናደዳለሁ፡፡ ሁሌም መቆጣት ስለሆነ ማንም ደፍሮ አይናገረኝም፡፡ እናቴ ብቻ ነች የምትነግረኝ፡፡ እሷን  ደግሞ መናገር አልችልም፡፡ ሁሉም ግን እንደሚያዝንብኝ ይገባኛል፡፡ 

አንዳንዴ በነገር ወጋ ያደርጉኛል፡፡ ብዙ ነገሮች አስቤ በተግባር የማውለው ግን ጥቂት ነው፡፡ አስቤ፣ አስቤ አንዳንዴ ፍርሃት፣ ፍርሃት ይለኛል፡፡ አንዴ በሬዲዮ አንድ የኤሌክትሪክ ፖል ወድቆ ሰው ገደለ የሚል ዜና ሰማሁ፡፡ ከዛን ጊዜ ጀምሮ ከመስሪያቤታችን ግቢ ያለው ፖል ቢወድቅ እኮ እኔ ላይ ነው የሚወድቀው ብዬ በተደጋጋሚ በማሰቤ ቀና ስል በመስኮቱ ፖሉን ካየሁት ስፈራ እውላለሁ፡፡ 

ሰዎችን ሳወራ የሆነ ነገር ካሉ በጣም ስለሚያሳስበኝ እንደድሮው ከሰዎች ጋር ማውራት አያስደስተኝም፡፡ ዝምተኛና ብቸኛ ሆኛለሁ፡፡ ይሄ ሁኔታዬ ደግሞ መልሶ ያስጨንቀኛል፡፡ ለዚህ መዓት መፍትሄ ይኖራችሁ ይሆን?

እኔ ነኝ

ask your doctor zehabesha

ውድ ጠያቂያችን ከፅሑፍህ እንደተረዳነው ያንተ ችግር ጭንቀት ነው፡፡ ጭንቀትና ከጭንቀት ጋር የተያያዙ ችግሮች በጣም የተለመዱና በብዛት የሚከሰቱ የአዕምሮ ህመም አይነቶች ናቸው፡፡ የተለያዩ ሪፖርቶች እንደሚያሳዩት እስከ 31 በመቶ የሚሆኑ የዓለማችን ህዝቦች በህይወታቸው ውስጥ ቢያንስ አንዴ የጭንቀት ችግር ያጋጥማቸዋል፡፡ ብዙ ጊዜ ግን ጭንቀት እንደ ችግር አይታይም ወይም ቢታም ተገቢው ህክምና አያገኝም፡፡ በነገራችን ላይ ጭንቀት የዕለት ተዕለት ኑሮአችን አካል ነው፡፡ ጭንቀት ችግር የሚሆነው የዕለት ተዕለት እንቅስቃሴያችን ማስተጓጎል ሲጀምር ነው፡፡ የስነ ልቦና ባለሙያዎች የጭንቀት ችግር (Anxiety disorder) ብለው የሚሉት ችግር ምልክቶችን  በሚገባ ዘርዝረው አስቀምጠዋል፡፡ የመጀመሪያው ምልክት የጭንቀት መጠኑ የበዛ (excessive) መሆኑ ብሎም ከፍራቻ (fear) ስጋት (worry) እና ነገራትን ማስወገድ (avoidance) ጋር የተያያዘ እንደሆነ ነው፡፡ ሌላኛው ምልክት ደግሞ ጭንቀቱ በማህበራዊ ህይወታችን፣ በስራችን ወይም በሌሎች የህይወት ዘርፎቻችን ላይ ከፍተኛ ጉዳት (significant distress) ወይም መስተጓጎል (impairment) ሲፈጥር ነው፡፡ ሌላው ደግሞ ግለሰቡ መጨነቁ ምንም ዋጋ እንደሌለው አምኖ እያለ ጭንቀቱን ማቆም አለመቻሉ ነው፡፡ ከእነዚህ በተጨማሪ ደግሞ የጭንቀት ሁኔታው ቢያንስ ለአራት ሳምንታት የቀጠለ መሆኑ፣ ተደጋጋሚ የሰውነት መወጣጠር መኖሩ፣ በሁኔታዎች በፍጥነት የመናደድ ሁኔታ በተደጋጋሚ መታየቱ እና ለመተኛት መቸገር የጭንቀት ችግርን ለመለየት የሚያስችሉት ምልክቶች ናቸው፡፡

በፅሑፍህ  ላይ የነገርከን ምንም ነገር ስለሌለ በመጀመሪያ ጭንቀትህ የተፈጠረው በሌሎች አካላዊ ወይም አዕሯዊ ህመሞች አለመሆኑን ማረጋገጥ ተገቢ ነው፡፡ የስነ ልቦና ባለሙያዎች እንደሚነግሩን እነ ስኳር፣ ልብድካምና የመሳሰሉ ስር የሰደዱ ህመሞች እና ከዚህ በፊት ያጋጠሙ የጭንቀት ችግር፣ ስሜት የመቀያየር ችግር (Mood disorder) ወዘተ አሁን ላለው የጭንቀት ችግር አስተዋፅኦ ያደርጋሉ፡፡ ከእነዚህ በተጨማሪም ለረዥም ጊዜ ብቻን መኖር (loneliness)፣ መጥፎ የአስተዳደግ ሁኔታ (Adverse parenting) እና በልጅነት ጊዜ የደረሱ ከፍተኛ ድንጋጤ የሚፈጥሩ ክስተቶች ለጭንቀት ችግር እንደሚያጋልጡ ባለሙያዎቹ አረጋግጠዋል፡፡

በመሆኑም እነዚህን መለየቱ በጣም ጠቃሚ ነው፡፡ ምክንያቱም የችግሮችህ ምንጮች እነዚህ ነገራት ከሆኑ ለእነሱ የሚሰጠው የመፍትሄ አቅጣጫና ለጭንቀት ችግር የሚሰጠው የመፍትሄ አቅጣጫ የተለያየ ስለሆነ፡፡ በመሆኑም ቀጥለን የምንሰጥህ የመፍትሄ አቅጣጫ በእነዚህ ምክንያቶች የመጣ ከሆነ ብዙ የሚያግዝህ ስለማይሆን ችግርህን እንደገና ፃፍልን ወይም በአካባቢህ ያሉ ካውንስለሮችን አነጋግር፡፡ ያንተ ችግር በእነዚህ ምክንያቶች ያልወጣ ከሆነ ግን ቀጥለን የምንጠቁምህን የመፍትሄ አቅጣጫዎች ተግብራቸው፡፡

የመፍትሄ አቅጣጫዎች

ውድ ጠያቂያችን በፅሑፍህ ላይ ከጠቀስካቸው ነገሮች ተነስተን ያንተ ችግር አጠቃላይ የጭንቀት ችግር (Generalized Anxiety Disorder) ተብሎ የሚጠራው የጭንቀት ችግር አይነት ነው፡፡ ይህ ችግር ደግሞ የሚመጣው ከተሳሳቱ የአስተሳሰብ ሂደቶች (faulty thoughts) ነው፡፡ ስለሆነም እነዚህን የተሳሳቱ አስተሳሰቦን መለየቱ የመጀመሪያ መፍትሄ ይሆናል፡፡

ምንም እንኳ የተለያዩ አይነት የተሳሳቱ የአስተሳሰብ ሂደቶች ቢኖሩም ከአንተ ሁኔታ ጋር ይያያዛሉ ያልኳቸውን ዋና ዋና ሂደቶች ልጠቁምህ፡፡ አንደኛውና ባንተ ፅሁፍ ላይ በግልፅ የሚታየው አዕምሮን ማንበብ (mind reading) የሚባለው ሲሆን ይህም ሰዎች ስለኛ የሚያስቡትን አውቃለሁ የሚል አስተሳሰብ መያዝ ማለት ነው፡፡

ለምሳሌ አንተ ሁሉ እንደሚያዝንብኝ አውቃለሁ የሚል አስተሳሰብ ይዘሃል፡፡ ይህ የተሳሳተ አስተሳሰብ ነው ምክንያቱም ሁሉም ስለሚፈሩኝ አይነግሩኝም ካልክ በኋላ እንዴት እንደሚፈሩህ እወቅ ብትባል የምትመልሰው አዕምሮአቸውን አንብቤ ነው የሚሆነው፡፡ አዕምሮን ማንበብ ደግሞ እንዲሁ እንደቀላል የሚቻል አይደለም፡፡

ሁለተኛው ደግሞ ሁሉም ወይም ምንም አይነት አስተሳሰብ (all none thinking) የሚባለው ነው፡፡ ይህም ማለት ሁሉም ነገሮች እንደፈለግነው እንዳሰብነው መሆን አለባቸው ካልሆኑ ግን ሁሉም አልተሳኩልኝም ብሎ ማሰብ ማለት ነው፡፡

የሰው ልጅ ምሉዕ ስላልሆነ ሁሉንም እንደፈለገው እንዳሰበው ማድረግ አይችልም፡፡ ይልቁንም ካሰባቸው ውስጥ አንዳንዱ ይሳካሉ፣ አንዳንዱ ደግሞ አይሳካም፡፡ ስለሆነም ይህንን አስተሳሰብ የያዙ ሰዎች የተሳሳቱ አስተሳሰብ ይዘዋል ይባላል፡፡

ነገሮችን ወደ ራስ ማዞር (personalization) የሚባለው ደግሞ ሌላኛው የተሳሳተ አስተሳሰብ ነው፡፡ ይህ ማለት ከእኛ ጋር ተያያዥነት የሌላቸውን ነገራት ሁሉ ከራሳችን ጋር የማያያዝ ሁኔታ ነው፡፡ ለምሳሌ በመንገድ እየተጓዝን ሰዎች ሲስቁ በእኔ ነው የሳቁ ብሎ ማሰብ ነገሮችን ወደ ራስ የማዞር አስተሳሰብ ነው፡፡ ጠያቂያችን ሆይ ቀደም ብዬ እንደገለፅኩት የመጀመሪያ ተግባርህ ጊዜ ወስደህ እላይ የጠቀስኳቸውንና ሌሎችንም የተሳሳቱ አስተሳሰቦችህን መፈተሽ ነው፡፡ እስኪ እራስህን ይህንን ጥያቄ ጠይቅ፡፡ ‹‹ለመሆኑ አንድ ሰው እንዴትስ ሆኖ ስለሁሉም ነገር ሊያስብ ይችላል?›› መልሱ ደግሞ ወደ ቀጣዩ ተግባር ይመራሃል፡፡

ቀጣዩ ተግባር ደግሞ አንተ ልታስብባቸውና መፍትሄ ልታመጣባቸው የምትችላቸውን እና ማሰብህ ለውጥ ሊያመጣባቸው የማይችሉ ጉዳዮችን ነጥለህ በፅሑፍ ማስፈር ነው፡፡ ለምሳሌ ስለ ዓለም ሙቀት መጨመር ስታስብ ብታድር ልታመጣ የምትችለው የመፍትሄ አቅጣ አለ? ስላቋረጥከው ትምህርት አስበህ ልታመጣ የምትችለው የመፍትሄ አቅጣጫ አለ? እንደዚህ እያደረክ ልታስብባቸው የሚገቡ ጉዳዮችን (area of concern) አይተህ አስቀምጥ፡፡ ልታስብባቸወ የማይገቡ ጉዳዮችንም ለይና ለብቻ አስቀምጥ፡፡ ልታስብባቸው የሚገቡ ጉዳዮችን አንድ በአንድ እያነሳህ በጥልቀት በማሰብ የመፍትሄ አቅጣጫ አስቀምጥላቸው፡፡

ለምሳሌ ስለ ትምህርት ጉዳይ አንተን ወክዬ ባስብልህ የማስቀምጠው የመፍትሄ አቅጣጫ ትማርበት የነበረው ትምህርት ተቋም ሄደህ የዊዝ ድሮል ፎርም መሙላትና በቀጣዩ ዓመት ትምህርትህን እንደገና ካቋረጥክበት መቀጠል ይሆናል፡፡ ቀጣዩ ተግባርህ የመፍትሄ አቅጣጫዎን ወደ ተግባር ለመቀየር መንቀሳቀስ ነው፡፡ ያን እንዴት እንደምትከውን ከመጠቆሜ በፊት አንድ ነገር ላንሳና የመፍትሄ አቅጣጫ ልጠቁምህ፡፡ በአዕምሮአችን ውስጥ ያሉ ሃሳቦ ተያይዘው ስለሚቀመጡ (schema ይባላሉ) አንድ ጉዳይ አንስተህ ለማሰብ ስትሞክር ሌሎች ሃሳቦች አብረው ተከታትለው በመምጣት ትኩረትህን ሊቀይሩ ይችላሉ፡፡

በዚህ ጊዜም ማድረግ ያለብህ በመጀመሪያ ትኩረትን ወደ ምትፈልገው ሃሳብ ለማድረግ መጣር፣ ይህ ሲከብድህ ደግሞ ማሰቡን ትተህ የተለያዩ የመፍታቻ መንገዶች (relaxation techiniques) መጠቀም፡፡ ለምሳሌ ከተቀመጥክበት ተነስተህ እጅና እግርህን እጥፍ ዘርጋ በማድረግ ማንቀሳቀስ ወይም ከዚህ በፊት ያዝናኑህ የነበሩ ነገሮች ማከናወን (ለምሳሌ ወክ ማድረግ፣ ሻይ ቤት ሄደህ ሻይ ቡና ማለት፣ ፊልም ማየት፣ ወዘተ)፡፡ በዚህ አለ በዚያ ሌሎቹ ሃሳቦች መተው ጭንቀትህን ሲጨምሩብህ ትኩረትህን ወደ ሌላ አቅጣጫ መቀየሩ በጣም ጠቃሚ ተግባር ነው፡፡

አሁን ደግሞ አስበህ የመፍትሄ አቅጣጫ ያስቀምጥክባቸውን ጉዳዮ እንዴት መከወን እንዳለብህ ልጠቁምህ፡፡ አጠቃላይ የጭንት ችግር ያለባቸው ሰዎች ችግራቸው እየተባባሰ የሚሄደው በአዕምሮአቸው ብዙ ነገራትን ያስቡና ወደ ትግበራው ሲመጡ የቱን ትተው የቱን እንደሚተግብሩ ስለሚያስጨንቃቸው ነው፡፡ ለዚህ የመጀመሪያው መፍትሄ የሚያስቡባቸውን ጉዳዮ ብዛት መቀነስ ሲሆን ቀደም ብዬ የጠቀስኳቸውን ተግባራት በመከወን ጉዳዮን መቀነስ ትችላለህ፡፡ ያም ሆኖ ግን ለእነዚህ ጉዳዮ ያስቀመጥካቸው የመፍትሄ አቅጣጫዎች በራሳቸው ብዙ ይሆኑና ወደ ጭንቀት ሊመልሱህ ይችላሉ፡፡ ለዚህ ደግሞ መፍትሄው ተግባራቱን በዝርዝር በወረቀት በማስፈር ባላቸው ጥቅም (importance) እና አስቸኳይነት (urgency) መሰረት በቅደም ተከተል ማስቀመጥ (prioritization) አለብህ፡፡ ከዛም ሳምንታዊ እቅድ ታወጣና በጣም አስፈላጊና አስቸኳይ የሆኑትን በመጀመሪያው ሳምንታዊ እቅድህ ታስገባቸውና ለመተግበር ትሞክራለህ፡፡ በቀጣይ ሳምንት እቅድህ ደግሞ በመጀመሪያው ሳምንት ያላሳካቸሃቸውንና በቅደም ተከተልህ መሰረት ሌሎች ተግባራትን አካተህ ለመተግበር ትሞክራለህ፡፡

በዚህ ሁኔታ ስትቀጥል የሚያስጨንቁህን ነገራት በሙሉ መፍትሄ ወስደህባቸው ጭንቀትህን መቀነስ ትችላለህ፡፡ በስተመጨረሻ አንድ ነገር ልበልህና ፅሑፌን ላጠናቅቅ፡፡ አጠቃላይ የጭንቀት ችግር ለብዙ ጊዜ የቆየባቸው ሰዎች ነገሮችን ማድረግ እችላለሁ የሚል እምነታቸው (self efficacy) ከጊዜ ወደ ጊዜ እየቀነሰ ይመጣል፡፡ አንተ በዚህ ችግር ምን ያህል እንደቆየህ ባትነግረንም ይህ እምነትህ እንደቀነሰ መገመት እንችላለን፡፡ ነገሮችን ማድረግ እችላለሁ የሚል እምነትን ለመጨመር ሁለት መንገዶች አሉ፡፡ አንደኛው ሁሉንም ነገራት መከወንን በአንዴ በመጀመር በአንዴ እምነታችንን በከፍተኛ ሁኔታ ማሳደግ (Boost) ነው፡፡

ሌላኛው ደግሞ እምነታችንን ቀስ በቀስ የማሳደግ ሁኔታ ነው፡፡ አንተ የፈለከውን መንገድ መምረጥ ትችላለህ ነገር ግን ሁለተኛው በአብዛኛው ውጤታማ ስለሆነ እሱን መጠቀምህ የተሻለ ነው ባይ ነኝ፡፡ በነገርህ ላይ አንድ ትንሽ የሆነች ተግባር እንኳ ማድረግ አለብኝ ብለህ ወስነህ ስትተገብራት ማድረግ እችላለሁ የሚለው ስሜትህ ሲለወጥ ታስተውላለህ፡፡

ለምሳሌ ሁሌ ወደ ስራ ስትሄድ ማስቲካ የመግዛት ልምድ ኖሮህ ነገ መግዛት የለብኝም ብለህ ወስነህ ሳትገዛ ስራ ከሄድክ ማድረግ እችላለሁ የሚለው እምነትህን አድጎ ሌሎችንም ነገራት አደርጋለሁ ብዬ ከተነሳሁ አደርገዋለሁ የሚል እምነት ይፈጥርብሃል፡፡ በመሆኑም ቀላል ከሚባል ተግባራት በመጀመር ቀስ በቀስ ሁሉንም ተግባራት የመከወን እምነትህን አጎልብት እያልኩ የዛሬ ፅሑፌን በዚህ አጠቃለልኩ፡፡ መልካም የለውጥ ጊዜ!

The post Health | ‹‹በጭንቀት እየተሰቃየሁ ልሞት ነው፤ መፍትሄውን ጠቁሙኝ›› appeared first on Zehabesha Amharic.

ቁርሾ |እውነተኛ የወንጀል ታሪክ

$
0
0

 

Revange

ይህ ታሪክ ለብዙዎች ድራማ እስኪመስላቸው ድረስ ሲያስገርማቸው የኖረ ታሪክ ነው፡፡ በሀገራችን በአብዛኛው ብሔሮች ዘንድ ሰፍኖ የኖረው ቂም በቀልና የጥቁር ደም ባህል ምን ያህል የሰው ልጅን አርቆ አሳቢነት እንደሚፈትንና ከሰብአዊ አስተሳሰብ እንደሚያወጣ ጭምር የሚመሰክር የወንጀል ታሪክ ነው ይሉታል ብዙዎች፡፡ ከአስር ዓመት በፊት የተፈፀመ ቢሆንም ወንጀሉን መዝግቦ የተቀመጠው ሰነድ ግን አሁን ድረስ ለሁሉም መማሪያ የሚሆነውን ቁም ነገር አስቀርቷል፡፡

1980 .

ደራ

ሰሜን ሸዋ

ፍቼን ተሻግሮ ጀሊሳን አልፎ ወደ ጎሐፅዮን በሚወስደው መንገድ ላይ የሚመጣው ደራ ከተማ ለስሙ ከተማ ይባል እንጂ የመሰረተ ልማትም ሆነ ለከተማ ብቁ የሚያስብለው መዋቅር የተሟላለት ስፍራ አይደለም፡፡ ደራ የሚኖሩትን ሰዎ የታችኞቹን ህዝቦች ‹ደሮዬ› ብለው ይጠሯቸዋል በተለምዶ፡፡ ደሮዬዎች በአብዛኛው የአማራ ተወላጆች ሲሆኑ ‹ቆፍጣናና እንቢ ባይነት ባህሪያቸው የሆነ ነው› ይሏቸዋል ሲገልጿቸው፡፡ ከደገምና ከጀሊሳ አካባቢ ያሉ ሰዎች ሲመራቸውና ከሰው ተጣልተው ደም ሲቃቡ የሚሸሹት ወደዚህ ደራ ነው፡፡ ምክንያቱ ደግሞ ደራ ጥቅጥቅ ያለ ጫካ የነበረው ስፍራ በመሆኑ ለመሸፈት የሚመች አካባቢ ስለሆነ ነው፡፡ ደራ በአካባቢው ባሉ የኦሮሞ ተወላጆች ዘንድ እንደ ጀግና ምሽ የሚታይ ጫካ ነበር፡፡ (የዛሬን አያድርገውና)፡፡ ብዙዎች የጀግኖች ጀግና ነው እያሉ የሚያሞካሹትና በአፄ ኃ/ሥላሴ ጊዜ የነበረውን ግፍ ተቃውመው ከሸፈቱት የአካባቢው የኦሮሞ ተወላጆች አንዱ የነበረው ሀገሬ ቱሉ መደበቂያ ቦታ ነበር ይላሉ፡፡ ሀገሬ ቱሉ በአብዛኛው የደገምና አካባቢው ነዋሪ ዘንድ ‹የድሃ ጠበቃ› ሲባል በሌሎች ዘንድ ደግሞ ዘራፊ ሽፍታ ነው ይሉታል፡፡ እዚያ ደራ ጫካ ውስጥ መሽጎ የአካባቢውን ጭቃ ሹሞችና ባለቤቶች ድንገት አደጋ ጥሎ እየገደለና እየዘረፈ ለሌሎች ያከፋፍል ነበር ይባላል- ሀብትና ከብት፡፡

በዚህ አካባቢ ልማድ ጥቃት ክፉ በትር ነው፡፡ ባለነፍጥ የሆነው ህዝብ በደም ከተፈላለገ ያንን የጥቁር ደም ሰንሰለት የሚበጥስ አንዳች ነገር የለም፡፡ የለገሰ በዳ ታሪክም የሚመዘዘው ከዚሁ የመጠላለፍና የመጠባበቅ ማህበራዊ ተራክቦ ውስጥ ነው፡፡ ለገሰ በዳኔ በ1980 ዓ.ም የ26 ዓመት ወጣት ሆኗል፡፡ ነገር ግን እሱ የ2 ዓመት ልጅ ሳለ በ1956 ዓ.ም አካባቢ አባቱ በዳኔ  ቱፋ እንዴት ህይወታቸው እንዳለፈ በአክስቱ ሲነገረው የኖውን ዕውነት ነው ይዞ ያደገው፡፡ እነሆ ያ ታሪክ፡፡

1956 ዓ.ም

መስከረም ወር

ደገም አካባቢ ባሉ የኦሮሞ ተወላጆች ዘንድ በታላቅ ጉጉት ይጠበቅ የነበረው የመስቀል በዓል እየተቃረበ ነው፡፡ ገና ነሐሴ አጋማሽ ላይ ክረምቱ ግም ብሎ እንደገባ ግም ብሎ እየወጣ ሳለ ነው አካባቢው በአደይ አበባና በለምለም ሜዳው ፍንትው ብሎ የሚታየው፡፡ ይህ የአዲስ ዘመን መምጫ ብስራት ለመቀበልና ለማቀባበል ወጣቶቹ ዱላቸውን ይዘው ጅራፋቸውን እያጮሁ ‹‹መስቀላ ሞቲን አያና›› ይላሉ፡፡ የኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮቹ የአካባቢው ነዋሪዎች ይህን የመስቀል በዓል ለማክበር ቀድመው የሚዘጋጁትና እየጨፈሩ የሚዘልቁት ቢያንስ ከ16 ቀን በላይ ለሆነ ጊዜ ነው፡፡ የመጨረሻው የመስቀል በዓል እስኪከበር ድረስ፡፡ ከዘመን መለዋጫ በዓለም በላይ የሆነ ክብር ያለውን ይህንን ቀን ለማክበር ወዲህ ወዲያ ሲሉ ከነበሩት ወጣቶች አንዱ ደግሞ በዳኔ ቱፋ ነው፡፡

በዳኔ የተዳረው ገና የ18 ዓመት ወጣት ሳለ ነው አባቱ ቱፋ ጎዳና በአካባቢያቸው የታወቁ ገበሬ ናቸውና በሰው ዘንድ ያላቸው ክብር የላቀ ነበር፡፡ ምንም እንኳን ዘራቸው ከባላበትና ከፍ ካለው የኦሮሞ ብሔር ወገን ባይሆንም አቶ ቱፋ በኃይለኝነታቸው የሚነካቸውና የሚደርስባቸው የሌላቸው የተከበሩ ሰው ናቸው፡፡ እኚህ ሰው ከወለዷቸው አራት ልጆች መካከል አንደኛው ልጅ ብቻ ወንድ ሲሆን ሶስቱ ሴቶች ናቸው፡፡ በኦሮሞ ባህል ወንድ ልጅ ሲወለድ በከፍተኛ ስነ ስርዓትና በጥይት ተኩስ ነው ደስታ የሚገለፀው፡፡ ወንድ የወለደ አባት ‹‹የወንድ አባት›› ተብሎ ይከበራል፡፡ ይህ ኩራትም አቶ ቱፋ ቤት ገባ፡፡

ልጃቸውን በዳኔ አሉት፡፡ ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ሙሉ መሆን የቻሉት የመሰላቸው፡፡ ለዚህ ነው በዳኔን በቶሎ የዳሩት፡፡ በዳኔ ወንድ ልጅ ወልዶ ለማየት የነበራቸው ህልም እንደተመኙት ከሁለት ዓመት በኋላ ተሳካላቸው፡፡ የ20 ዓት  ልጅ ሳለ ካገባት ኮረዳ የመጀመሪያውን ልጅ አገኘ፡፡ በቤተሰቡ ዘንድ ደስታና ፌሽታ ሆነ፡፡ ለገሰ አሉት ይህን ልጅ፡፡ አቶ ቱፋ በዓይናቸው ሁለት ወንድ ልጆቻቸውን አይተው ደግሞ ሌላ እንዲመጣላቸው በመመኘት ላይ ሳሉ ነው ያልታሰበ ነገር የተፈጠረው፡፡ ልጃቸው በዳኔ አደጋ ውስጥ ወደቀ፡፡

በዚያን የፀደይ ወር መስከረም ጠብቶ መስቀል ሞቲን አያና ተከብሮ ሲያልቅ አንድ ሰው በበዳኔ ላይ ዓይኑን ጣለ፡፡ በዳኔ ገና የ22 ዓመት ወጣት ሳለ ሚስቱም ሁለተኛ ልጇን በፀነሰችበት ወቅት ቱሉ ሲጠብቀው የነበረው ቀን መጣለት፡፡ በዳኔን አብዝቶ ይጠላው ነበርና አንድ ቀን ከዚህች ዓለም ጋር ያለውን የኮንትራት ሕይወት ሊያቆራርጥበት አጥብቆ ይመኝ ነበር፡፡

የዚህ ምክንያቱ ደግሞ የበዳኔ ሚስት ናት፡፡ ጊፍቲ በአካባቢው ጎልማሶች ዘንድ ዓይን ውስጥ የገባችና ያም ይሄም የኔ በሆነች ብሎ የሚሳሳላትና የሚመኛት ሴት ነበረች፡፡ ይህች ወጣት ገና በ16 ዓመቷ ሊያገቧት የሚራኮቱባትን ጎረምሶች በመፍራት ከቤቷ ሳትወጣ ያደገች ናት፡፡ ይህ የመጣው ደግሞ አባቷ የተላከባቸውን ‹ልጅዎን ለልጄ› የሚል ጥያቄ ሁሉ አይሆንም ብለው በመመለሳቸው ሳቢያ ነው፡፡ ከጎረምሶቹ ሁሉ አብልጦ ይወዳት የነበረው ቱቦ በአባቱ በተመረጡለት ሽማግሌዎች አማካኝነት ልጅቷን አስጠይቆ የግሉ ለማድረግ ያደረገው ጥረት አልተሳካለትም፡፡ ምንም አማራጭ አልነበረውም፡፡ በቁጭትና በንዴት መሀል ሆኖ አንድ ቀን ውጪ ቢያገኛት እንደሚጠልፋት እያሰበ ሳለ አስደንጋጭ ወሬ ሰማ፡፡ በዳኔ ሊያገባት ነው ተባለ፡፡ በዳኔ በእኒያ ባለግርማ ሞገስ አባቱ የተነሳ የተመኘው ተሳክቶለት የጊፍቲን አባት ስምምነት አግኝቷል፡፡ የጊፍቲ አባት ለአቶ ቱፋ ‹ልጅን ለልጄ› የሚል ጥያቄ አሉታዊ ምላሽ የሚሰጡበት ጊዜ አልነበራቸውም፡፡

ለስንቱ ከልክዬ እችላለሁ ብለው ለሚያከብሯቸው ወዳጃቸው ልጅ ፈቀዱ፡፡ በአካባቢው ይህ ጉዳይ ወሬ ሆኖ ተሰማ፡፡ ቱሉ አንጀቱ አረረ፡፡ በበዳኔ ሰርግ ጊዜ የአጨዳ ስራ አለብኝ ብሎ በማሳበብ በሰርጉ ላይ ሳይገኝ ቀረ፡፡ ወደ ሌላ ከተማ ዘልቆ ነበር የጠፋው፡፡ ከዚያን ጊዜ ጀምሮ እሱም ሳያገባ በዳኔም የወንድ ልጅ አባት ሆኖ ሁለተኛ ልጁን ሊደግም ሲጠባበቅ ሳለ ነው ቱሉ ንዴት የገነፈለበትና ራሱን መቆጣጣር ያቃተው፡፡ የመስቀል በዓል ተከብሮ እንዳለቀ መስከረም 22 ቀን የሆነው ሆነ፡፡

ቱሉ አደፈጠ፡፡ በዳኔ ደግሞ ጀሊሳ ወደተባለ መንደር የሚወርድበት ጉዳይ እንዳለው መረጃ ደርሶታል፡፡ ከ6 ሰዓት ያላነሰ የሚያስኬደው የእግር መንገድ ተከትሎ ብቻውን እያንጎራጎረ ወደ መንገዱ የገባው በዳኔ ከ30 ደቂቃ በላይ ሳይጓዝ ነው ድንገት ጭው ባለው አፋፍ ላይ ቱሉ ከች ያለበት፡፡ ቱሉ በዳኔ ፊት ለፊት ቺኮዝ ጠመንጃውን ወድፎ ሲቆም በዳኔ ዓይኑን ተጠራጠረ፡፡ ቱሉ ሊገድለው እስኪፈልግ ድረስ ቂም ይይዝብኛል ብሎ አልገመተም፡፡ ይህን ቢያውቅ አባቱ ለገሰን ሲወልድ የሰጡትን ጠመንጃ ይዞ በወጣ- ለዚያውም ውውል ጠመንጃ፡፡ ግን አልሆነም፡፡ ተቀደመ፡፡

በአንድ ጥይት ደረቱን የበሳው ተኩስ የኋልዮሽ ቁልቁለቱ ላይ ዘረረው፡፡ የአካባቢው ወፎች በርግገው እስኪጠፉ ድረስ በድምጿ እየሰነጠቀችው ጥይት በበዳኔ ልብ ላይ ከተሳበች በኋላ ፀጥ አለች፡፡ ቱሉ ከአካባቢው ጫካ ጫካውን አቆራርጦ ተሰወረ፡፡ ከዚያ በኋላ አንድም ሰው አላወቀም፡፡ ቱሉ አረቄ ቤት ገብቶ ቀኑን ሙሉ ሲዘፍን ነበር የዋለው፡፡ የበዳኔ አስከሬን በነጋዴዎች ተገኝቶ ጉዳዩ ሲሰማ ጊዜ ግን አካባቢው ተተራመሰ፡፡

አቶ ቱፋ ጠመንጃቸውን ይዘው ወጥተው አገር ይያዝልኝ አሉ፡፡ ቱሉ ማንም ባይጠረጥረውም ሁኔታው ሲያስፈራው አመሻሹ ላይ ጠፋ፡፡ በማግስቱ የቱሉ ቀብር ላይ አለመኖር ሲታወቅ ነው ገዳዩ እሱ መሆኑ የተረጋገጠው፡፡ በዳኔ በታላቅ ስርዓት ታጅቦ በተኩስ ተጋግሎ በዋለ ቀብር ግብአተ መሬቱ ሲፈፀም የቱሉ ቤተሰቦችም በቁጣው ለመሸሽ ሀገር ለቀው ጠፉ፡፡ የበዳኔ ቤተሰቦች የቱሉን ወለጆች ቤትና ንብረት በእሳት አቃጥለው ከብቶቻቸውም ገድለው ጠፉ፡፡ አገሩ ተረባበሸ፡፡ ደራ ጫካ ቱሉ ተደብቆበታል ተብሎ ስለታሰበ ታመሰ፡፡ ልጁ ግን አልተገኘም፡፡

ከጊዜ በኋላ በቱሉ ጥፋት ወላጆች መቀጣት የለባቸውም ተብሎ ትልቅ ሽምግልና ተካሄደና የቱሉ ቤተሰቦች ወደቅያቸው እንዲመለሱ ተፈቀደ፡፡ ያም ሆኖ ስጋት ቤተሰቡን መጫኑ አልቀረም፡፡ ጥቁር ደም አንድ ዕለት ድንገት ለዚያ የፈሰሰ ደም በቀል ይህን ቤት ማንኳኳቱ እንደማይቀር ይታወቅ ነበር፡፡

ጊዜ የሁሉም ችግር መፍትሄ ነውና አቶ ቱፋ በልጃቸው ሞት የደረሰባቸውን ሀዘን መቋም ባለመቻላቸው ሳቢያ ህይወታቸው አለፈ፡፡ አሁን የቀሩት የሟቹ እህቶች ብቻ ናቸው፡፡ ዘመን እያለፈ በሄደ ቁጥር ወሬው የደበዘዘና የተረሳ መሰለ፡፡ ነገር ግን የሟችን ልጅ ለገሰ በዳኔን ባሳደገችው የሟች እህት ዘንድ ይህ ቂም አልረገበም፡፡

የቱሉን ቤተሰቦች ባየች ቁጥር ሁሌም ሟች ወንድሟ እየታሰባት እንደተሳቀቀች ኖራለች፡፡ ይህን ደግሞ ለህፃኑ ለገሰ እየነገረች አሳድጋዋለች፡፡ ‹‹የአባትህ ገዳዮች ቤት ያውልህ- የአባትህን ገዳይ አባት ይኸውል- ወደነርሱ አጠገብ እንዳትደርስ›› ወዘተ… እያለች ነበር ያሳደገችው፡፡ ለገሰ በዚህ የበቀል መርዝ ተመርዞ ነው ዕድሜውን የቆጠረው፡፡ አክስቲቱ አርፋ አልተቀመጠችም፡፡ አንዳንዴ ቱሉ እቤት መጥቶ ቤተሰቦቹ ጋር አድሮ ሌሊት ሄደ ሲባል እየሰማች- አንዳንዴ ታይቶበታል የሚባልበትን ቦታ እያጠናች ኖረች፡፡ አንድ ወቅት ግን ቱሉ ጫንጮ ውስጥ እንደሚኖር ደረሰችበት፡፡ ሚስት አግብቶ ቤት መስርቶ ይኖራል፡፡ ይህን የነገራት ደግሞ አንድ የደገም ተወላጅ የሆነ ወዳጇ ነው፡፡ አሁን የበቀል ጉማ የሚረከብበትን ወቅት አሰበች፡፡

1980 .

ለገሰ የ24 ዓመት ወጣት ሆኗል፡፡ አባቱን በዳኔን የመሰለ ጉብል፡፡ ፀጉሩና መልኩ ከእናቱ የተወረሰ ቁመናው ግን እንደ አባቱ የተዘነከተ ሰው፡፡ ይህን ጉልበትና በአባቱ በቀል ቂም የነደደ ልቡን ይዞ ተነሳ፡፡ አክስቱ መክራ ላከችው፡፡ በደንብ ያጠናችው የጫንጮን ከተማ አካባቢውን ሁሉ አስረግጣ ነግራ በመኪና ተሳፍራ ቦታውን አሳይታው ተመለሰች፡፡ የዘመናት ምኞቷ ሊሰምር መሆኑን አስባ በውስጧ ፈንድቃለች፡፡

1980 ሐምሌ ወር

ጫንጮ

አንድ ወጣት ኮስመን ያለ ገፅታውን ይዞ የነቱሉን ቤት አንኳኳ፡፡ የ48 ዓመት ጎልማሳው ቱሉ ነበር በር የከፈተው፡፡ በሩ ላይ የቆመው አሳዛኝ ገፅታ ያለው ወጣት በኦሮምኛ ‹‹እባካችሁ ከብት እረኛ ትፈልጉ ከሆነ ማደሪያ ስጡኝና አብሬያችሁ እየኖርኩ እረኛ ልሁን›› ብሎ ጠየቀ፡፡ ቱሉ በሩ ድረስ የመጣለትን ሲሳይ በዋዛ ሊያልፈው አልፈለገም፡፡ ልጁን አስገባው፡፡ ለእግሩ ውሃ ለሚባለው ደግሞ ትኩስ እንጀራ እንዲያመጡለት አዘዘ፡፡

ከዚያም ስለ አመጣጡ ሁኔታ ጠየቀው፡፡ ወጣቱ ከገብረጉራቻ መምጣቱንና ሥራ ፍለጋ ሲንከራተት መኖሩን ተናግሮ መጠጊያ ብቻ እንደሚፈልግ በመግለፅ የሰውየውን ቀልብ ሳበ፡፡ ከዚያ በኋላ የእረኝነት ስራውን በሚገባው መጠን መፈፀም ጀመረ፡፡ የቤተሰቡ አባላት ወደውት ልጆቹ እንደ ወንድማቸው አይተውት ቱሉም አቅርቦት እረኝነቱ 2 ወር አለፈው፡፡ ይህ ወጣት ለገሰ ነው፡፡

ከአክስቱ ጋር የነጋገረው ቀን ደረሰ፡፡ መስከረም 22 ቀን፡፡ ልክ አባቱ የሞተበት ቀን፡፡ ቱሉ በዳኔን የገደለበት ቀን፡፡ በዚያን ዕለት ደግሞ ቱሉ ጫንጮ እግዚአብሔር አብ ቤተክርስቲያን የሚሄድበት ጉዳይ ነበረው፡፡ ከዋናው መንገድ ራቅ ብሎ በማሳ ውስጥ ባለ ቀጭን መንገድ የሚያመራው የእግዚአብሔር አብ ቤተክርስቲያን ቱሉ ከሚኖርበት ስፍራ ራቅ ይላል፡፡ ለገሰ የዛሬው እረኝነቱ ነገር አለበት፡፡ ከብቶቹን ከቤት ያወጣቸው ገና በማለዳ ነው፡፡ 12፡00 ሰዓት በረት ከፍቶ ሲወጣ እነ ቱሉ ‹ጎበዝ› ብለውታል በልባቸው፡፡ ይህን ጉብዝናውን መስክረውለታል፡፡ እሱ ግን ዕቅድ አለው፡፡ ከብቶቹን በፍጥነት እያካለበ ሜዳ አደረሳቸው፡፡ ከዚያም ቶሎ ብሎ ተመለሰ፡፡ ወገቡ ውስጥ የሻጣት ጥልቆ መኖሯን አረጋግጧል፡፡ በጋቢው ሸፍኗታል፡፡ ቀኑ ጭጋግ ውጦታል፡፡ ይህ ደግሞ ለርሱ ተመችቶታል፡፡ በነቱሉ ቤት እና በቤተክርስቲያኑ መሀል የተዘረጋው መንገድ ላይ ዘወር ያለ ቁጥቋጦ የወረሰው ቦታ አለ፡፡ እዚያ ስፍራ ላይ ጥጉን ይዞ አደፈጠ፡፡ ለ1 ሰዓት ሩብ ጉዳይ ሆኗል፡፡

ቱሉ ፈጠን ፈጠን እያለ በቆቅ ዓይኑ አካባቢውን ገርመም እያደረገ ዱላውን በትከሻው አንግቶ መጣ፡፡ ከሩቅ ይታየዋል፡፡ ጎፈሬ ፀጉሩ አሁንም አስፈሪ አድርጎታል፡፡ ለገሰ ተዘጋጀ፡፡ ቱሉ እዚያ ቁጥቋጦ ዘንድ ደረሰ፡፡ በውስጥ እየቆራረጠ ሲያልፍ ድንገት ከተደበቀበት እመር ብሎ ወጣ ለገሰ፡፡

ያቺን ጥልቆ በእጅ ይዟል፡፡ በፍጥነት ላዩ ላይ ተከመረበት፡፡ ቱሉ ሳይዘጋጅበት ስለነበር ወደ ኋላ ወደቀ፡፡ ለገሰ አልራራም ቱሉ ዓይኑ እያየው የአባቴ በዳኔ ገዳይ አገኘሁህ ብሎ በጥልቆው ጭንቅላቱን መታው፡፡ ግንባሩ ለሁለት የተከፈለው ቱሉ ወዲያው ነበር የሞታው፡፡ ለገሰ የቱሉን ጎፈሬ በእጁ ጎትቶ ነጩና ኪሱ ከትቶ እየበረረ ወደ ጫንጮ ከተማ አመራ፡፡ እዚያ በቀጠሯቸው መሰረት የምትጠብቀውን አክስቱን አገኘ፡፡

‹‹የወንድሜን ገዳይ ገደልከው?››

‹‹አዎ አዳዶ ገድዬልሻለሁ››

‹‹በምን ልመንህ?››

‹‹ይኸው ፀጉሩ››

ከኪሱ አውጥቶ አሳያት፡፡ አቅፋ ሳመችው ተያይዘው ወደ ሀገራቸው ሄዱ፡፡

15 ቀናት በኋላ

ለገሰን ለመፈለግ ወደ ቤቱ የሄዱት የአካባቢው ታጣቂዎችና ፖሊሶች ገና የነለገሰ በር ሳይከፈት ነው የደረሱት፡፡ ዓለም ዘጠኝ ያሉትን እነለገሰንና አክስቱን በቤት እንዳሉ በቁጥጥር ስር ለማዋል ነበር እቅዱ፡፡ ውሻው ሲጮህ ግን የለገሰ አክስት በር ከፈተች፡፡ ተሰብስበው ስታያቸው ዘላ ገባችና በሩን ዘጋች፡፡ በዚህ መሀል የፀጥታ ኃይሎቹ በር ከፍተው ለመግባት ሲዘጋጁ ድንገት ከውስጥ የተኩስ ድምፅ ተሰማ፡፡ ያኔ ሁሉም መሳሪያቸውን አወጠና ጥግ ጥግ ያዙ፡፡ ለገሰ በጓሮ መስኮት ዘሎ ወጥቶ ጥሻው ውስጥ ሲመሽግ በጥይት አካባቢውን አመሱት፡፡ እሱም ተኮሰ፡፡ ብዙ አልቆየም ወዲያው ሲያቃስት ተሰማ፡፡ ተመታ፡፡ እዚያው የቤቱ ቢሮ ጓሮ ውስጥ ወደቀ፡፡ አልሞተም ነበርና ወደፍቼ ይዘውት መጡ፡፡ ይህን ሁሉ ቃል የተናገረው ሆስፒታል ሳለ ነው፡፡ ለ10 ቀናት ነበር በህይወት የቆየው፡፡ ከዚያ በኋላ ግን በጉዳቱ ሳቢያ አሸለበ፡፡ ፖሊሶች እዚህ ወጣት ላይ ያደረሱበት የቱሉ አባት የልጄ ገዳይ ለገሰ እንጂ ሌላ ማንም አይሆንም ብለው በማመልከታቸውና ለገሰ ለ3 ወር ከሰፈሩ ጠፍቶ መመለሱ በመታወቁ ነበር፡፡ አክስትየው ግን ለ3 ዓመታት ታስራ ተለቃለች፡፡ የበቀል ጦስ ሶስት ሰው ከዚህች ዓለም አሰናብቶ ተጠቃለለ፡፡ የሚቀጥል ይኖር ይሆን? ከ16 ዓመት በኋላም ቢሆን አሁንም የእነዚያ ሰዎች ቤተሰብ በስጋት መተያየቱን አላቆመም፡፡

The post ቁርሾ | እውነተኛ የወንጀል ታሪክ appeared first on Zehabesha Amharic.

አቶ ኤፍሬም ማዴቦ በትህዴን የወታደሮች ምርቃት በዓል ላይ ያደረጉት ንግግር –ቪዲዮ ከኤርትራ

ተዋናይቷ የኢትዮጵያን ሕዝብ ይቅርታ ጠየቀች

$
0
0

(ዘ-ሐበሻ) በዳና ተከታታይ የቴሌቭዥን ድራማ ላይ ታዋቂነትን ያገኘችው እና በቅርቡ ከቼክ ጋር በተያያዘ የማጭበበር ወንጀል ተከሳ ታስራ የተፈታቸው ተዋናይት ቤዛዊት መስፍን የኢትዮጵያን ሕዝብ ይቅርታ መጠየቋን ጋዜጠኛ ጌጡ ተመስገን ዘገበ::
bezawit mesfin

ተዋናይቷ እንዲህ የሚከተለውን መልዕክት አስተላልፋለች:-

“‹… ሰው በማመን፤ ባለማወቅ ጥፋት አጥፍቻለሁ፡፡ በጥፋቴ ስድስት ወራት ተፈረደብኝ፡፡ ለአራት ወራት የህግ ማረሚያ ቤት ቆይቻለሁ፡፡ ሁለት ወራት በአመክሮ ተቀነሶልኝ ተፈታሁ፡፡ … የማረሚያ ቤት ሕይወት በጣም ከባድ ነው፡፡ ማረሚያ ቤት ስገባ በልብ ሕመም በ22ዓመቷ ያረፈችው የእህቴ ሳምራዊት መስፍን ልጅ የማሳድገውን አናንያ ዳንኤል ጥዬ ነው የገባሁት፡፡ አያቴ (እታባ) ባትኖር ኖሮ አናንያ ምን ይውጠው ነበር? …”

ተዋናይት ቤዛዊት 6 ወር ተፈርዶባት በአመክሮ የተለቀቀችበት ወንጀል ከግብረ አበሯ ጋር በመሆን በተሰጣቸው የ4 ሺህ ብር ቼክ ላይ ከፊት ለፊቱ ሁለት ቁጥርን በመጨመር ያልተፈቀደላቸውን 24 ሺህ ብር ከወጋገን ባንክ ሰባራ ባቡር ቅርንጫፍ አውጥተዋል የሚል እንደነበር ከዚህ ቀደም በዘ-ሐበሻ ድረገጽ ላይ መዘገባችን ይታወሳል::

The post ተዋናይቷ የኢትዮጵያን ሕዝብ ይቅርታ ጠየቀች appeared first on Zehabesha Amharic.

Sport: የዛሬው የእንግሊዝ ፕሪምየር ሊግ ውጤቶች

$
0
0

arsenal
united

Updated – (ዘ-ሐበሻ) 13ኛው ሳምንት የ እንግሊዝ ፕሪምየር ሊግ ዛሬ ተካሂዷል:: የሳምንቱ መክፈቻ ጨዋታ ማን.ዩናይትድ ወደ ዋትፎርድ ሜዳ ወርዶ የተጫወተው ሲሆን ባለቀ ሰዓት በተገኘች ጎል 3 ነጥብ ይዞ ወጥቷል::

ፕሪሙሚየር ሊጉን በ13ኛው ሳምንት ጨዋታ ሲመራ የነበረው አርሰናል በዌስትብሮሚች 2ለ1 ተሸንፎ ወደ 4ኛ ደረጃ ወርዷል:: የዛሬው ጨዋታ ውጠቶች የሚከተሉት ናቸው::
ዋትፎርድ 1 – ማን.ዩናይትድ 2
ቸልሲ 1 – ኖርዊች 0
ኤቨእርተን 4 – አስቶንቭኢላ 0
ኒውካስትል 0 – ሌስተር ሲቲ 3
ሳውዝሃምፕተን 0 ስቶክ ሲቲ 1
ስዋንሳ 2 በርንማውዝ 2
ዌስት ብሮሚች 2 አርሰናል 1

ማንቸስተር ሲቲ በሜዳው እና በደጋፊው ፊት ሊቨርፑል 4ለ1 ተሸንፏል::

city

The post Sport: የዛሬው የእንግሊዝ ፕሪምየር ሊግ ውጤቶች appeared first on Zehabesha Amharic.

ኢትዮጵያ ራሷ ባዘጋጀችው የሴካፋ ዋንጫ የመክፈቻ ጨዋታ በብሩንዲ ተሸነፈች

$
0
0

ethiopia

(ዘ-ሐበሻ) የመጀመሪያው ቀን ጨዋታዎች አሰተናጋጇ ኢትዮጵያ በሩዋንዳ ፤ዛንዚባር በቡሩንዲ 1ለ 0 በሆነ በተመሳሳይ ውጤት ተሸንፈዋል።

በኢትዮጵያ አስተናጋጅነት ዛሬ የተጀመረው የ2015 ሴካፋ ዋንጫ (2015 CECAFA) ጨዋታ የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን በሜዳው እና በደጋፊው ፊት 1ለ0 በሆነ ውጤት ተሸንፏል::

ባለፈው ሳምንት በዲሞክራቲክ ኮንጎ በደርሶ መልስ ጨዋታ ተሸንፎ ከዓለም ዋንጫ ማጣሪያ ጨዋታዎች የተሰናበተው ብሄራዊ ቡድናችን አሁን ያለበት ወቅታዊ አቋም በስፖርት ቤተሰቡ ዘንድ መነጋገሪያ ሆኗል::

ብሔራዊ ቡድኑ ራሱ ባዘጋጀው ውድድር ላይ በሜዳው እና በደጋፊው ፊት 1ለ0 መሸነፉ አሳሳቢ መሆኑን የሚናገሩት የስፖርት ተንታኞች በየፊናቸው መፍትሄ የሚሉትን ሃሳቦች በመሰንዘር ላይ ናቸው::

በኢትዮጵያ ዛሬ በተጀመረው የሴካፋ ዋንጫ በሩዋንዳ 1ለ0 ስትሸነፍ ዛንዚባርም እንዲሁ በብሩንዲ በተመሳሳይ 1ለ0 ተረታለች::

ኢትዮጵያና ሩዋንዳ ያደረጉት ጨዋታ ከረፍት በፊት 0ለ0 ተጠናቆ ሩዋንዳዎች በ54ኛው ደቂቃ ላይ ያገኟትን የቅጣት ምት ወደ ጎል ቀይረው አሸንፈው ወጥቷዋል::

የዛሬው ጨዋታ በአዲስ አበባ ስታዲየም የተደረገ ሲሆን ውድድሩ በአዋሳና በባህርዳር ስታዲየሞች እንደሚቀጥሉ ለዘ-ሐበሻ የደረሱ መረጃዎች አመልክተዋል::

በኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን መሸነፍ የተናደደ አንድ ደጋፊ በዘ-ሐበሻ የፌስቡክ ገጽ ስሜቱን ሲገልጽ እንዲህ ብሏል

“ተከብረሽ የኖርሺው በሠውነት ቢሻው
ዮሃንስ መጣና አረገሽ እንዳሻው !”

The post ኢትዮጵያ ራሷ ባዘጋጀችው የሴካፋ ዋንጫ የመክፈቻ ጨዋታ በብሩንዲ ተሸነፈች appeared first on Zehabesha Amharic.

የወንድ ዘር ቀድሞ መፍሰስ ችግር መንስኤው ምንድን ነው? መፍትሄውስ?

$
0
0

malin Jirra

የወንድ ዘርፈሳሽ ቀድሞ መፍሰስየወንድ ዘር ፈሳሽ ቀድሞ መፍሰስ የሚከሰተዉ አንድ ወንድ በግብረ ስጋ ግንኙነት ወቅት እራሱ ወይም የትዳር/የፍቅር አጋሩ ሳይፈልጉ ቀድሞ ማፍሰስ ካለ ነዉ፡፡ ግምቶች ቢለያዩም ይህ ሁኔታ ከ3 ወንዶች ዉስጥ በአንዱ ላይ ሊታይ ይችላል፡፡ ችግሩ ሁልጊዜ የማይከሰት ከሆነ ግን አሳሳቢ አይደለም፡፡የወንድ የዘር ፈሳሽ ቀድሞ መፍሰስ ችግር አለ የምንለዉ

♢ሁሌ ወይም ብዙዉን ጊዜ የወንዱ ብልት በሴቷ ብልት ዉስጥ በገባ በአንድ ደቂቃ ዉስጥ የወንድ ዘር ከፈሰሰ
♢ ሁሌ ወይም ብዙዉን ጊዜ በግብረ ስጋ ግንኙነት ወቅት የወንድ ዘር መፍሰስን ማቆየት/ማዘግየት ካልተቻለ
♢ጭንቀትና በራስ ያለመተማመን ስሜት በመፈጠሩ ፆታዊ ግንኙነት ላለማድረግ መፈለግ ካለስነልቦናዊና ባዮሎጂካል ጉዳዮች ለወንድ ዘር ፈሳሽ ቀድሞ

መፍሰስ መከሰት ምክንያት ሊሆኑ ይችላሉ፡፡ ምንም እንኳ ብዙ ወንዶች ስለ የወንዶች የዘር ፈሳሽ ቀድሞ መፍሰስ ችግር ለማዉራት ቢያሳፍራቸዉም ይህ ጉዳይ በጣም ብዙ ጊዜ የሚከሰትና በቀላሉ ሊታከም የሚችል ነዉ፡፡ መድሃኒቶች፣የምክር አገልግሎትና የግብረስጋ ግንኙነት ቴክኒክ ወይም የእነዚህ ድብልቅ የወንድ ዘር ፈሳሽ ቀድሞ መፍሰስን ሊያሻሽሉ ይችላሉ፡፡

የወንድ ዘር ፈሳሽ ቀድሞ መፍሰስ ችግር በሰዉየዉ የህይወት ዘመን ያለ(ፕራይመሪ) ወይም አኳየርድ(ሰከንደሪ) ተብሎ በሁለት ይከፈላል፡፡ በህይወት ዘመን ያለ(ፕራይመሪ) የወንድ ዘር ፈሳሽ ቀድሞ መፍሰስ ችግር የሚጀምረዉ አንድ ወንድ የመጀመሪያዉን የግብረስጋ ግኑኙነት ካደረገበት/ከጀመረበት ጊዜ አንስቶ ያለ ሲሆን ሁለተኛዉ አይነት ደግሞ በመጀመሪያዎቹ ጊዜያት ያለምንም ችግርየግበረስጋ ግንኙነት ሲያደርግ ቆይቶ ከጊዜ በኃላ የዘር ፈሳሽ ቀድሞ መፍሰስ ችግር ሲገጥሞት የሚመጣ ነዉ፡፡ብዙ ወንዶች ምንም እንኳ ከላይ በተገለፀዉ መሰረት የወንድ ዘር ፈሳሽ ቀድሞ መፍሰስ ችግር ባይኖራቸዉም ይህ ችግር እንዳላቸዉ አድርገዉ ይወስዳሉ፡፡ የህክምና ባለሙያ ማማከር የሚገባዎ መቼ ነዉ?ብዙዉን ጊዜ/በተደጋጋሚ በግብረስጋ ግንኙነት ወቅት የወንድ ዘር ፈሳሽዎ እርስዎ ካቀዱት ጊዜ በፊት አስቀድሞ የሚወጣ ከሆነ ምንም ሳያፍሩ የህክምና ባለሙያዎን ማማከር ያስፈልጋል፡፡ አንዳንድ ጊዜ ብቻ/አልፎ አልፎ የሚከሰት የዘር ፈሳሽ ቀድሞ መፍሰስ ችግር ምንም ችግር የሌለዉ ስለሆነ መጨነቅ አያስፈልጎትም፡፡ለወንድ ዘር ቀድሞ መፍሰስ ችግር ምክንያቶች ለዚህ ችግር ምክንያት የሆነ ይህ ነዉ የሚባል ትክክለኛ መንስኤ የለዉም፡፡ ነገር ግን የሚከተሉት ምክንያቶች ይጠቃሳሉ፡፡ ስነልቦናዊ ምክንያቶችየተወሰኑ የህክምና ባለሙያዎች እንደሚሉት ከሆነ ቀድሞ የነበረ የግብረስጋ ግንኙነት ልማድ ለመቀየር አስቸጋሪ ሊሆን ይችላል፡፡

እነሱም:-
♢ማንም እንዳያዮት በመፈለግና በቶሎ የእርካታ ጣሪያ ላይ ለመድረስ መቸኮል
♢በግብረስጋ ግንኙነት ወቅት በፍጥንት እንዲያደርጉ የሚያደርግዎ የጥፋተኝነት ስሜት የሚሰማዎት ከሆነሌሎች

ለወንዶች ዘር በቶሎ መፍሰስ ምክንያት ሊሆኑ የሚችሉ ነገሮች፡-
♢የወንዶች ብልት ያለመቆም ችግር ካለ
♢መረበሽ/ ጭንቀት ካለ
♢ከትዳር ወይም ፍቅር አጋርዎ ጋር የመስማማት ችግር ካለ

ባዮሎጂካል ምክንያቶችየሚከተሉት ምክንያቶች ሊጠቀሱ ይችላሉ፡-
♢የሆርሞን መጠን መዛባት
♢በጭንቅላት/አዕምሮ ዉስጥ ያሉ ኒዩሮትራንስሚተርስ መጠን መዛባት
♢የወንዶችን የዘር ፈሳሽ መረጨትን የሚቆጣጠረዉ ዘዴ ላይ ችግር መኖር
♢የታይሮይድ ሆርሞን መዛባት
♢በፕሮስቴት ዕጢ ወይም በዩሬትራ ላይ ኢንፌክሽንና መቆጣት መከሰት
♢በዘር የሚወረስ
♢በአደጋ ወይም ቀዶ ጥገና ምክንያት የነርቮች መጎዳት ምንም እንኳ የወንዶች የዘር ፈሳሽ ቀድሞ መፍሰስ ችግር ብቻዉን በጤናዎ ላይ የሚያመጣዉ ጉዳት ባይኖርም/ባይጨምርም በግል በህይወትዎ ላይ የሚያጣው ከፍ ያለ እንደ
♢ጭንቀትንና የትዳር/ፍቅር ግንኙነትዎን ማወክ
♢የልጅ ያለመዉለድ ችግርን ሊያስከትል ይችላል፡፡የሚደረጉ የጤና ምርመራዎች
♢የጤና ባለሙያዎ ከሚጠይቅዎ የግብረ ስጋ ግንኙነት ታሪክዎ በተጨማሪ ከዚህ በፊት ስለነበርዎ የጤና ታሪክና አካላዊ ምርመራ ሊያደርግልዎ ይችላል፡፡ በተጨማሪም የሽንትና የደም ምርመራና የሆርሞን ምርመራዎችን ሊያደርግልዎ ይችላል
♢አንዳንዴ ደግሞ ወደ የስነ አዕምሮ ስፔሻሊስት ባለሙያና ዩሮሎጂስትጋ ሊልኮት ይችላል፡፡የወንዶች ዘር ፈሳሽ ቀድሞ መፍሰስ ህክምና ለወንዶች የዘር ፈሳሽ ቀድሞ መፍሰስ ሊሰጡ የሚችሉ ህክምናዎች ብዙ ምርጫዎች ያሉት ሲሆን እነዚህም ባህሪን የመለወጥ ዘዴ፣ ቶፒካል አንስቴቲክስ፣ በአፍ የሚዋጡ መድሃኒቶችና የምክር አገልግሎትን ሊያጠቃልል ይችላል፡፡ መገንዘብ የሚገባዎት ነገር ቢኖር የትኛዉ የህክምና ዘዴ ለእርስዎ እንደሚሰራ ለማወቅ የተወሰነ ጊዜ ሊወስድ ይችላል፡፡ የባህሪ ዘዴየህክምና ባለሙያዎ በእርስዎ ላይ በግንኙነት ወቅት ያለዉን ጫና ለመቀነስ ለተወሰነ ጊዜ የግብረስጋ ግንኙነትን እንዲተዉና በሌሎች የወሲባዊ ጨዋታዎች እንዲተኩት ሊያደርጎት ይችላልዘ ፖዝ ስክዊዝ ቴክኒክ/ዘዴይህን ዘዴ እርስዎና የትዳር/ፍቅር አጋርዎ በሚከተለዉ መንገድ ሊተገብሩት ይችላሉ፡-

1. እንደተለመደዉ የግብረ ስጋ ግንኙነትን መጀመርና የዘር ፈሳሽዎ ለመዉጣት እስከሚሰማዎ ድረስ መቀጠል
2. የዘር ፈሳሹ ሊመጣ ሲል ብልትዎን ከአጋርዎ ብልት ዉስጥ በማውጣት የትዳር/ፍቅር አጋርዎ የብልትዎ ጭንቅላትና አንጓ በሚገናኝበት ቦታ ላይ የዘር ፈሳሹ የመዉጣት ስሜት እስኪጠፋሎት ድረስና የዘር ፈሳሹ እንዳይወጣ ለተወሰነ ሰከንዶች ተጨምቆ እንድያዝልዎት ማድረግ
3. የዘር ፈሳሹ የመዉጣት ስሜት ካለፈልዎ በኃላ ለ30 ሰኮነዶች ያህል መቆየት፤ከዚያን እንደገና ለግብረስጋ ግንኙነት መሟሟቅ (foreplay)፤ ብልትዎ በሚጨመቅበት ወቅት የመቆሙ ጥንካሬ ሊቀንስ ይችላል፡-ይህ ግን የግብረስጋ ግንኙነት መነቃቃት በሚፈጠርበት ጊዜ አንደገና ስለሚጠነክር ሊያሳስቦት አይገባም

4. አሁንም በድጋሚ ግንኙነትዎን ከጀመሩ በኃላ የዘር ፈሳሹ የመዉጣት ስሜት ሲሰማዎ በድጋሚ ብልትዎን ከአጋርዎ ብልት ዉስጥ በማዉጣት በድጋሚ ጨምቆ ስሜቱ እስኪያልፍ ድረስ መያዝ ይህን መንገድ በተደጋጋሚ በመሞከር በግንኙነት ወቅት ብልትዎን ወደ ትዳር/ፍቅር አጋርዎ ዉስጥ በሚያስገቡበት ወቅት የዘር ፈሰሽ በቶሎ መፍሰስን ከመከላከሉም በላይ ከተወሰኑ ልምምዶች በኃላ እንዴት የወንድ ዘር የመፍሰስን ስሜት ብልትዎን ከትዳር/ፍቅር አጋርዎ ብልት ዉስጥ አዉጥተዉና ጨምቀሁ መያዝ ሳያስፈልግዎ ማዘግየት እንደሚችሉ ልምድ እየሆነ እንዲመጣ ይረደዎታል፡፡የምክር አገልግሎትይህ ቶክ ቴራፒ የሚባለዉ ሲሆን ስለራስዎ የግብረስጋ ግንኙነት ሁኔታና ልምድ ከስነአዕምሮ ባለሙያዎ ጋር የሚወዩበት ህክምና ዘዴ ነዉ፡፡ ይህ በእርስዎ ላይ በግብረስጋ ግንኙነት ወቅት የሚከሰተዉን ጭንቀት(ፐርፎርማንስ አንዛይቲ) ለመቀነስና ከጭንቀት ጋር ተያይዞ የሚመጣዉን ችግሮች ለመቀነስ የተሻለ መንገድ እንዴት መፈለግ እንደሚችሉ ያግዞታል፡፡ ይህ የህክምና ዘዴ ከሌሎች የህክምና ዘዴዎች ጋር አብሮ ቢሰጥ የተሻለ ዉጤት ያስገኛል፡፡መድሃኒቶችየወንዶችን የዘር ፈሳሽ ቀድሞ መፍሰስን ችግር ሊያዘገዩ የሚችሉ የተለያዩ መድሃኒቶች ያሉ ሲሆን እነርሱም በብልት ላይ የሚቀቡና በአፍ የሚዋጡ ናቸዉ፡፡ የትኛዉ መደሃኒት ቢሰጥዎ ዉጤት እንደሚያመጣ ለማወቅ የህክምና ባለሙያዎን ማማከር ያስፈልጋል፡፡

The post የወንድ ዘር ቀድሞ መፍሰስ ችግር መንስኤው ምንድን ነው? መፍትሄውስ? appeared first on Zehabesha Amharic.


Health |መንታ ምንጮች |የእናት ጡት ወተት ለጤናማ ልጆች ዕድገት (ልዩ ዘገባ)

$
0
0

የሰባት ወር ህፃን ነበረች፡፡ በእናቷ እቅፍ ውስጥ ሆና በዕለተ ቅዳሜ ከቀኑ ስምንት ሰዓት ላይ ድንገተኛ ክፍላችን ከች አለች፡፡ እናት ‹‹ልጄን አድኑልኝ!›› እያለች መጮህ ጀመረች፡፡ ያው ድንገተኛ ክፍላችን ክፍል ውስጥ መስማት ከለመድናቸው ቃላቶች አንዱ ነው፡፡ ቢሆንም ግን ንቁ ነበርን፡፡ ህፃናት ደርሰው ቅጠል የሚሆኑት ነገር ስላለ እንደ ሐኪም ህፃናትን የማናምነው ነገር አለ፡፡ ህፃኗን ተቀበልንና አልጋ ላይ ጋደም አደረግናት፡፡ ጥያቄዎች ቀጠሉ፡፡ ‹‹ምን ሆና ነው?›› እናት ፍርሃት በጠፈነገው አንደበት ‹‹ተቅማጥ! ትናንት እኮ ብዙ አልነበረም፡፡ ጠዋትም ሥራ ስገባ ሰላም ነበረች፡፡ ታዲያ ከስራ ስመለስ ሠራተኛዋ ተቅማጡ እየባሰባት መሆኑን ነገረችኝ፡፡ አንስቼ ሳያት ደካክማብኝ አገኘኋት›› እውነትም ሕጻኗ ሙሽሽ ብላ ነበር፡፡ ዓይኗ ሰርጉድ ብለዋል፤ ቆዳዋ ሲጨበጥ ዘግይቶ ነበር የሚለጠጠው፡፡ እጆቿና እግሮቿ እንቅስቃሴያቸው ተገተው ፍፁም መፍዘዝ ውስጥ ነበረች፡፡ ልቧ ሊወጣ ደርሷል፡፡ ትንፋሾቿ ቁርጥ ቁርጥ ይላሉ፡፡ ሞት ጥላውን ያጠላባት ምስኪን ህፃን!! አሁን ይህቺን ነፍስ ለማዳን ሩጫ ተጀመረ፡፡

Breast Feading

አንዱ ክብደቷን ለካ፡፡ አንዱ የሚሰጣትን ፈሳሽ ያዘጋጃል፡፡ ሌላው የኦክስጂኑን ቱቦ ወደ አፍንጫዋ ከተተ፡፡ ደም ስሯን ማግኘት የደም ቧንቧዎች ሁሉ ደብዛቸው ጠፋ፡፡ ስለዚህ ወደ ሁለተኛው አማራች መሸጋገር ግድ ሆነ፡፡ የእግሯን አጥንት በስተን ህይወቷን ከሞት አፋፍ ሊነጥቅ የሚችለውን ፈሳሽ መስጠት የግድ ነበር፡፡ ነገሩ ሳይደግስ አይጣላም ሆነና ተሳካ፡፡

እነዚያ ህይወት አድን ጠብታዎች ወደ አጥንቷ እየተንዶለደሉ መግባት ቀጠሉ፡፡ የዚህችም ህጻን ነፍስ ደግሞ ኃይልን ነስታ ማንሰራራት ጀመረች፡፡ የተዘጋጀው ፈሳሽ በስድስት ሰዓታት ውስጥ አለቀ፡፡ በመትረፏ  እርግጠኞች ሆንን፡፡ ሌሎች ተጓዳኝ ምርመራዎች ግን ቀጥለው ነበር፡፡ የደም ምርመራዋ መካከለኛ የሆነ ደም ማነስ እንዳለባት አሳበቀ፡፡ ምክንያቱ ደግሞ የብረት እጥረት መሆኑ ተደርሶበት ደሟን ሊተካ የሚችል ሽሮፕ ለሶስት ወራት ሰጠናት፡፡ የአመጋገቧን ነገር እናትን ጠየቅን፡፡ ጡት ብቻ እስከ ሶት ወር ጠባች፡፡ ከዚያ ጊዜ በኋላ እናት የመንግሥት ሠራተኛ ስለሆነች ጡት ማጥባት አመቺ ሆኖ ስላላገኘችው የላም ወተት ጀመረችላት፡፡

ብቻ ይገርማል! የሰው ህይወት በሰከንዶች ሽርፍራፊ ታሪኩ ሊለወጥ ነገሩ ሊገለበጥ የሚችል ፍጥረት መሆኑ፡፡ ታዲያ አንድ የጥያቄ እጅ የአዕምሮዬ በር ስታንኳኳ ሰማኋት፡፡

የዚህች ህፃን ችግር ከአንድ መሰረታዊ ጥያቄ ጋር የተያያዘ መሆኑን፡፡ ይኸውም የሚገባትን የእናት ጡት በየጊዜው አለማግኘቷ ከተፈጠረባት ችግር ጋር ሊያያዝ ይችላል፡፡ የዛሬው ፅሑፍ የእናት ጡት ወተትን በተመለከተ ሰፋ ያለ ማብራሪያ ለመስጠት ይሞክራል፡፡

አንድ እውነት ልንገራችሁ፡፡ ሩሲያና አሜሪካ እንደ ድሯቸው አብረው ቢሰሩ እንኳን የእናትን ሁለት ጡቶች ያህል ለህፃኑ ጠቃሚ የሆነ ወተት ሊፈጥሩ አይችሉም፡፡ ዓለምን ሊያጠፋ የሚችል ሚሳኤል ፈጥረዋል፡፡ የመንታ ምንጮችን ያህል ግን የህፃኑን ጥያቄ አልመለሱም፡፡ ‹‹ለመሆኑ ምን አይተህበት ነው እንደዚህ እነዚህ ሁለት ሀገራቶችን የደፈርከው?›› በሉኝ፡፡ ምክንያቴን እንደሚከተለው አቀርባለሁ፡፡

የእናት ጡት ወተት ለህፃናት የሚሰጠው ጥቅሞች

1. የጨጓራንና የአንጀትን ዕድገትና እንቅስቃሴ ያፋጥናል

የእናት ጡት ወተት የህፃኑን ጨጓራና አንጀት ከማጎልበት በተጨማሪ ውስጡ  በሚይዛቸው ነገሮች የተነሳ አንጀትን በተለያዩ ተዋህስያን እንዳይወረሩ ማድረግ ይችላል፡፡ በዚያው ልክ ለሰውነታችን ተስማሚ የሆኑ ወዳጅ ባክቴሪያዎች እንዲያድጉ በማድረግ ከጠላት ባክቴሪያዎች የህፃኑን ጨጓራ እንዲጠብቁ ያደርጋል፡፡ ይሄ ነገር እምብዛም በላም ወተትም ሆነ በዱቄት ወተት ዳብሮ አይገኝም፡፡ በዚህ ምክንያት በህፃናት ላይ የሚከሰተውን የተቅማጥ በሽታ ይቀንሳል፡፡

2. ከትንፈሳ ጋር የተያያዙ በሽታዎችን ይቀንሳል፡፡

3. ዱቄት ከሚጠቀሙ ሰዎች ይልቅ የእናት ጡት ወተት የሚጠቀሙ ህፃናት ለጆቾ ቁስለት በሽታ የመጋለጥ ዕድላቸው አናሳ ነው፡፡ የሽንት ቧንቧ ኢንፌክሽንንም ቢሆን በመቀነሱ ረገድ የማይናቅ አስተዋፅኦ አለው፡፡

4. የእናት ጡት ወተት ወደ ፊት የሚፈጠርን ቅጥ ያጣ ውፍረት ይቀንሳል፡፡

5. ከልብና ቧንቧ ጋር የተያያዙ በሽታዎችንም ቢሆን ይቀንሳል፡፡

6. ለስኳር በሽ ያላቸውን ተጋላችነትም ይቀንሳል፡፡ ለምሳሌ፣ የላም ወተትን የሚጠቀም ህፃን ካለበላም ወተት ውስጥ ለሚገኘው ቤታ ካሴይን ለተባለው ፕሮቲን የሚለቀቀው የሰውነት መከላከያ ኢንሱሊን አምራች የሆነውን መረጭ ስለሚጎዳው ህፃኑ ለስኳር በሽታ የመጋለጥ ዕድሉ ይጨምራል፡፡

7. የእናት ጡት ወተት ህጻናት በደም ካንሰርና ለሌላ በልጆች ላይ የሚከሰትን ካንሰር የመቀነስ አቅም አለው፡፡

እናት ልጇን ጡት በማጥባቷ ለራሷ የምታገኛቸው ጥቅሞች

1. ከወለደች በኋላ ያለው የማህፀን ደም መፍሰስን ይከላከላል፡፡

ምክንያቱም ህፃነት በሚጠቡበት ጊዜ ኦክሲቶሲን የተሰኘው ሆርን ይመነጫል፡፡ ይህ ሆርሞን ደግሞ የማህፀን ጡንቻ እንዲኮማተር በማድረግ የማህፀን መሸብሸብ በማምጣት የደም መፍሰስን ይቀንሳል፡፡ በነገራችን ላይ ይህ ሆርሞን ነው ምጥን የሚያመጣው፡፡ ህዝባችን በተለምዶ የምጥ መርፌ ይለዋል፡፡ በጉልኮስ ውስጥ ተጨምሮ በነጠብጣብ መልኩ ወደ እናትየዋ ደም ሲገባ ምጥ ከተደበቀበት ከች ይላል፡፡ ምክንያቱም ማህፀንን ማኮማተር ደስ ይለዋል፡፡

2. የእርካታዋን ጊዜ ያሰምርላታል

ኦክሲቶሲን የተሰኘው ሆርሞን በፍቅር ውስጥ ከፍተኛ የሆነ ሚና እንዳለው ተገልፆልናል፡፡ እሱ ብቻ ሳይሆን ጥንዶች ሩካቤ በሚፈፅሙበት ጊዜ ይህ ሆርን መንጭቶ ደስታን ያጎናፅፋቸዋል፡፡ ልክ እንደዚህ ሁሉ ህፃኑ በሚጠባበትም ጊዜ ይህ ሆርሞን ይመነጫል፡፡ አንዱ ዓላማው ወተቱን ማፍለቅ ሲሆን ሁለተኛ አላማው ደግሞ በእናትና በህፃኑ መካከል ያለውን ትስስር ማጠንከር ነው፡፡ እጅግ ደስተኛ ያደርጋታል፡፡ ለልጇ ያላትን ጉጉት ይጨምረዋል፡፡

3. እንደ ወሊድ መቆጣጠሪያ ያገለግላታል

የዓለም የጤና ድርጅት (WHO) ባደረገው ጥናት ጡት ብቻ ለስድስት ወር የሚያጠቡ እናቶች በስድስቱ ወር ውስጥ የማርገዝ ዕድላቸው 1.2 በመቶ ነው፡፡ ከ100 እናቶች ውስጥ አንዷ ብቻ ታረግዛለች እንደ ማለት ነው፡፡ እስከ ስድስት ወር ባለው ጊዜ ውስጥ ጡት ማጥባትን ለወሊድ መቆጣጠሪያ መጠቀም የምትፈልግ ካለች ልጇን ለስድስት ወር መደበኛ በሆነ ጊዜ ውስጥ ጡት ብቻ ማጥባት ይኖርባታል፡፡

ቢሆንም ግን ያለውን ችግር ማለት አንድ ፐርሰንቷንም ቢሆን ለመቀነስ አብዛኛው የህክምና ባለሙያዎች ለሶስት ወር ብቻ ይህን ስልት እንዲጠቀሙ ይመክራሉ፡፡

4. ጡት የምታጠባ እናት በጡትና በእንቁልጢ (Ovary) ካንሰር የመጠቃት ዕድሏን በእጅጉ ትቀንሳለች፡፡

5. ከወጪ አንፃርም ቢሆንም ጡት ማጥባት እጅጉን ተመራጭ ነው፡፡ አሜሪካ ውስጥ በተደረገ ጥናት ዱቄት ወተት ከሚጠቀሙት ይልቅ የሚያጠቡት እናቶች 1000 ዶላር በየዓመቱ ይቆጥባሉ ተብሏል፡፡

እንዴት እናጥባቸው?

የዓለም የጤና ድርጅት (WHO) ህፃናት የመጀመሪያ ስድስት ወር ምግባቸው ጡት ብቻ እንዲሆን ደንግጓል፡፡ እናትን ሌሎች ምክንያቶች ካልገደቧት በቀር፡፡ ለምሳሌ ከ6 ወር በፊት የላም ወተት ቢጀምሩ የህጻናቱ አንጀት ያልዳበረ ስለሆነ የሚገባው የላም ወተት የአንጀት ግድግዳቸውን ጎድቶ ለአንጀት ኢንፌክሽን ከማጋለጡ በተጨማሪ የብረት ማዕድን በሚገባ እንዳይመጠጥ ስለሚያግድ ለደም ማነስ ያጋልጣቸዋል፡፡ መግቢያችን ላይ ያላቸውን ህፃንን አስታውሷት! ስለዚህ በመጀመሪያው ስድስት ወር ጡት ብቻ መጥባት ይኖርባቸዋል፡፡ ራሳቸውን ከደም ማነስና ከአንጀት ኢንፌክሽን ለመጠበቅ ብቻ ሳይሆን ከጡት ወተት የሚገኘውን ጥቅም ለማግኘት ሲሉ የእናት ወተት ብቻ በዚህ ጊዜ እንዲጠቡ ይመከራል፡፡

ህፃናት መጥባት መጀመር ያለባቸው በተወለዱ በአንድ ሰዓት ውስጥ ቢሆን ይመረጣል፡፡ ይህም የመጥባት አቅማቸውን ያሳድገዋል፡፡ እሱ ብቻ ሳይሆን የእናትየዋ ገላ ከህፃኑ ገላ ጋር መነካካት የራሱ የሆነ በጎ ጎን አለው፡፡ በ‹‹ኦፕሬሽን›› የሚወልዱ እናቶች ህፃናቱ በተወሰነ መልኩ ለጊዜው ፍዘት ሊያጋጥማቸው ይችላሉ፡፡ ይኸውም የማደንዘዣው ተፅዕኖ ነው፡፡ በእርግጥ ይህ የሚከሰተው ለኦፕሬሽ ግልጋሎት የዋለው ጠቅላላ ማደንዘዣ ከሆነ ነው፡፡ ነገር ግን አብዛኛውን ጊዜ ከእንብርት በታች የሚያደነዝዘውን መንገድ ስለሆነ የሚጠቀሙት ህፃናት በማደንዘዣው ተጽዕኖ ስር አይወድቁም፡፡ ይህም ቢሆን ቶሎ መጥባት እንዲጀምሩ ማበረታት የተገባ ነገር ነው፡፡

የአጠባባቸው መንገድ

ለመጀመሪያ ጊዜ የምትወልድ እናት የማጥባት ችግር ያጋጥማታል፡፡ በደንብ ማጥባት ካልቻለች ደግሞ ለእርሷም ሆነ ለልጇ ሰላም አይሰጥም፡፡

– በመጀመሪያ ህጻኑን እንዴት አድርጋ በእጇ ይዛ ማጥባት እንደምትችል (Posioning) እገልፀዋለሁ፡፡

– ሁለተኛው ደግሞ ህፃኑ እንዴት አድርጎ የጡቷን ጫፍ መያዝ እንዳለበት እንመለከታለን፡፡

1. ህጻኑ በታችኛውና በላይኛው ከንፈሩ መካከል አፉን ሲከፍት 120 ዲግሪ መስራት አለበት፡፡

2. የታችኛው ከንፈሩ ወደ ውጪ መገልበጥ አለበት፡፡

3. የህፃኑ አገጭና አፍንጫ ከጡቱ ጋር በጣም መቀራረብ አለበት፡፡

4. ጉንጩ ሙሉ ሆኖ መታየት አለበት፡፡

5. የህፃኑ ምላስ ከታችኛው ድዱ ወይም ጥርሱ በላይ ሆኖ ወደፊት ትንሽ መውጣት አለበት፡፡

ህፃኑ የጡቱን ጫፍ በስርዓት ላለመያዙ ምልክቶች፡-

1. የላይኛውና የታችኛው ከናፍር በአፍ ጠርዝ (comer of mouth) መገኛነት፡፡

2. የሰረጎደ ጉንጭ

3. የምላሱ ጫፍ ከእናትየዋ ጡት ጫፍ በታች አለመታየት፡፡

4. ካጠባች በኋላ የማሸብሸብ የጡት ጫፍ፡፡

ምን ያህል ጊዜ በቀን ይጥቡ?

የአመጋገቡ መጠን እንደ እናትየዋ የጡት ወተት  መጠንና የህጻኑ የመጥባት አቅም ሊወሰን ቢችልም በተለይ በመጀመሪያዎቹ ሁለት ሳምንታት ውስጥ ከ8-12 ጊዜ በቀን ሊጠቡ ይገባል፡፡ እናትየው በምታጠባበት ጊዜ የመጨረሻው ወተት እስኪወጣ ድረስ በደንብ ማጥባት አለባት፡፡ ምክንያቱም የመጨረሻው ወተት በስብ ፀጋ የተጥለቀለቀ ስለሆነ ፈጣን የሆነ ዕድገት ለህፃኑ ያጎናፅፈዋል፡፡ ስለዚህ በአንድ ጊዜ አንደኛዋን ጡት ብቻ እንዲጠባ በማድረግ የመጨረሻ ወተቱን እንዲያገኝ ማድረግ አለባት፡፡

የእናት ጡት ወተት በባህሪው ህጻኑን እንቅልፋም የማድረግ አቅም አለው፡፡ ስለዚህ ህፃናት እንቅልፋቸውን በመለጠጥ ይታወቃሉ፡፡ ወደው አይደለም፡፡ እንቅልፍን እየጠጡ ስለሆነ ነው፡፡ ስለዚህ ህፃኑ በእንቅልፍ ምክንያት ሳይጠባ አራት ሰዓት ካለፈው እናቴ ሆይ! ቀስቅሺና አጥቢው፡፡

ህጻኑ መራቡን እንዴት ልወቀው?

ህፃኑ መራቡን እንዴት ልወቀው የሚል ጥያቄ ተነስቷል፡፡ ጥሩ ጥያቄ ነው፡፡ ህፃናት እየተራቡ የሚግደረደሩት ጉድ የላቸውም፡፡ እንደ እኛ ይሉኝታ የለባቸውም፡፡ ግን አፍ አውጥተው ራበን አይሉም፡፡ ስለዚህ ምን እናድርግ?

የመራብ ምልክቶች (Feeding Cues)

1. እጃቸውን ወደ አፋቸው ማስጠጋት ወይም ማንቀሳቀስ

2. እጃቸውን መጥባት

3. መነጫነጭ

4. እጅና እግራቸውን ማወዛወዝ ወይም የመቅዘፍ አይነት እንቅስቃሴ ማሳየት፡፡

5. ማሚ በእነዚህ አራት ምልክቶች የማትረዳ ከሆነ የመጨረሻ ምልክታቸውን ያሳያሉ፡፡ ‹‹እሪ›› ብሎ ማልቀስ! መቼስ እናት ልጇ ስታለቅስ ተረት አታነብለትም፡፡ በልዩ ፍቅሯ ከመንታ ምንጮቿ በአንደኛው የልጇን ጥም ታረካለች እንጂ፡፡

የመጥገብ ምልክቶች

‹‹ልጅ ሆዴን አመመኝ እንጂ ጠገብኩኝ አያውቅም›› የሚል ብሂል አለን፡፡ ይሄ ተረት አፉን ለፈታ ህጻን ሊሆን ይችላል፡፡ ዛሬ ለተለወደው ህፃንስ ምን መፍትሄ አለ ካላችሁ የሚከተለውን ነገር አስታውሱ፡፡

1. ህፃኑ በራሱ ጊዜ የጡቱን ጫፍ ይለቃል፡፡

2. የፊቱና የእጆቹ ጡንቻዎች ሲረግቡ ይስተዋላል፡፡

3. ከሁለትና ሶስት ወር በታች የሆኑ ህፃናት ወደ እንቅልፍ አለማቸው ይመለሳሉ፡፡

በቂ የሆነ የጡት ወተት እያገኙ መሆናቸውን በምን እንወቅ?

1. የሚወስዱት መጠን

ከላይ እንደተገለፀው በመጀመሪያ ሁለት ሳምንታት ከ8-12 ጊዜ በቀን መውሰድ ሲኖርባቸው የመጥባት ችሎታቸው እየዳበረ በሚመጣበት ሶስተኛና አራተኛ ሳምንታት ከ7-9 ሊቀንስ ይችላል፡፡ አንዴ በሚጠቡበት ጊዜ ከ10-15 ደቂቃ በመጀመሪያው ሁለት ሳምንታት ሊወስድ ይችላል፡፡ ወራቸው እየገፋ ሲመጣ ግን ከ8-10 ደቂቃ በቂ ሊሆን ይችላል፡፡

2. ክብደታቸውን በተመለከተ

ህፃናት ገና እንደተወለዱ ባለው የመጀመሪያ ሳምንት ከ5-7 በመቶ የሚደርስ የክብደት መቀነስ ይገጥማቸዋል፡፡ ለምሳሌ፣ ሶስት ኪሎ የሆነ ህፃን ሩብ ኪሎ ሊቀንስ ይችላል፡፡ ከሁለተኛው ሳምንት ጀምሮ ግን ከ15-40 ግራም የሚደርስ ጭማሬ በየቀኑ ያገኛል፡፡ ነገር ግን ከ7 በመቶ በላይ ቅናሽ እያመጣ ያለ ህፃን ልዩ የሆነ ምርመራ ያስፈልገዋል፡፡

3. የሽንታቸው መጠን

የሽንታቸው መጠን ከቀን ወደ ቀን እየጨመረ ይመጣል፡፡ በመጀመሪያው 24 ሰዓት አንድ ጊዜ ሲሸኑ፣ በሁለተኛው ቀን ከ2-3ጊዜ፣ በ3ኛውና በ4ኛው ቀን ከ4-6 ጊዜ፣ ከ5ኛው ቀን በኋላ ከ6-8 ጊዜ ይሸናሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡ ስለዚህ የሽንታቸው ድግግሞሽ ከቀነሰ፣ ደማቅ ቢጫ ሽንት ከሸኑ ወይም ቀያይ ጠብ የሚመስሉ ደቃቅ ነገሮች፣ ከሽንታቸው ጋር ተቀላቅሎ ከወጣ እየወሰዱት ያለው የጡት መጠን በቂ አለመሆኑን ጠቋሚዎች ናቸው፡፡

4. ካካቸውን በተመለከተ

የመጀመሪያው ሶት ቀኖች ካካቸው ደማቅ ጎመኔ ቀለም ይኖረዋል፡፡ ከአራተኛው ቀን ጀምሮ ቢጫና የተፈረፈረ ወደ መሆን ይቀየራል፡፡ ነገር ግን ጥቁር እንደሆነ የሚቀጥል ከሆነ የአጠባቡ ችሎታው ገና ያልዳበረ መሆኑን ወይመ በቂ ጡት እየመነጨለት አለመሆኑን ሲያመለክት፣ ሲከፋ ደግሞ የአንጀት መዘጋትን ሊያመለክት ይችላል፡፡

አረንጓዴ ካካ፡- አንዳንዴ ህጻናት አረንጓዴ ካካ ይኖራቸዋል፡፡ መቼስ ጡት ብቻ የሚጠባ ህጻንን ካካው አረንጓዴ የሆነው ጎመን በልቶ ነው ብለን ስሙን አናጠፋም፡፡ ምክንያቱ እንዲህ ነው፡፡ ቅድም ስለመጨረሻው ወተት ሲያነቡ ነበር፡፡ የዚህ ወተት ሌላው ጥቅሙ ከፍተኛ የሆነ ስብ በውስጡ ስለያዘ የአንጀትን እንቅስቃሴ በማዘግየት ወተቱ ትንሹ አንጀት ላይ ላክቶስ የተባለው ካርቦ ሃይድሬት በደንብ እንዲፈጭ  ያደርጋል፡፡ ነገር ግን እናትየው የአንዱ ጡቷ ወተት በደንብ ተጠብቆ ሳያልቅ የምትቀይረው ከሆነ የመጨረሻውን ወተት ህጻኑ ሳያገኝ ይቀራል፡፡ ስለዚህ የአንጀት እንቅስቃሴው ፈጣን ስለሚሆን ብዙ ላክቶሶች /ወተት ውስጥ ያለ ካርቦሃድሬት/ ትልቁ አንጀት ላይ እንዲደርሱ ያደርጋል፡፡ እዚያ የሚገኙት ባክቴሪያዎች ደግሞ የሚፈጥሩት ጋዝ ካካውን አረንጓዴ ቀለም ይዞ እንዲወለድ ያደርገዋል፡፡ ስለዚህ እናቶች በዚህ ሊደነግጡ አይገባም፡፡ ይልቁንም ጡታቸውን በሚገባ ማጥባት ይኖርባቸዋል፡፡

በአጠቃላይ ህፃናት በቀን ከሶስት ጊዜ በላይ ካካ ሊኖራቸው ይችላል፡፡ ስለዚህ እስከ ስድስት ወር ጡት ብቻ ለህፃኑ መስጠት ቁርጥንና ክትፎን ያስንቃል ተብሎ ይታመናል፡፡ ነገር ግን በቂ የሆነ የጡት ወተት ማመንጨት ካልቻለች የዱቄቱን ወተት ልትጠቀም ትችላለች፡፡ በቂ አለመሆኑንም ልታውቅ የምትችልበት መንገዶች እነኚህ ናቸው፡፡

1. ከ7% በላይ ክብደት መቀነስ ካለው

2. የሽንቱ ወይም የሰገራው መጠን መቀነስ  ካለው ዱቄቱን በጥብጣ ልትሰጠው ትችላለች፡፡

የዱቄት ወተት እየበጠበጠች በምትሰጥበት ጊዜ ግን የጡቷን ወተት ያገኘችውን ያህል መስጠት ይኖርባታል፡፡ ምክንያቱም የጡት ወተት በወጣ መጠን የመተካቱና፣ የቀጣዩ ጡት ወተት የመጨመር መጠኑ እየጨመረ ስለሚመጣ ነው፡፡

ጡት ማጥባት የሚከለከልበት ጊዜ አለወይ?

መልሳችን አዎ ነው፡፡

1. የኤች.አይ.ቪ ቫይረስ በደሟ ያለ እናት ጡት ብቻ የምታጠባ ከሆነ እስከ ስድስት ወር ድረስ ማጥባት ትችላለች፡፡ ተጨማሪ ምግብ መስጠት ስትጀምር ግን ሙሉ ለሙሉ ማጥባቷን ማቆም ይኖርባታል፡፡

2. እናትየዋ የቲቢ በሽተኛ ከሆነች መድሃኒቱን ከጀመረች እስከ ሁለት ሳምንት ድረስ ማጥባት አትችልም፡፡ ምክንያቱም በምታስልበት ጊዜ ባክቴሪያው ወደ ህፃኑ እንዳይተላለፍበት ነው፡፡ በሌላ አባባል እናትና ልጅ መገናኘት አይችሉም፡፡ ጡቷ ግን እየታለበ ህጻኑ ሊጠቀምበት ይገባል፡፡

3. የጡት ቁስለት ሊያመጣ የሚችል ኸርፐስ የተባለ በሽታ አለ፡፡ ከህጻኑ አፍ ጋር ሲነካካ ቫይረሱ ሊተላለፍበት ይችላል፡፡ በሽታው በባለሙያ ይታወቃል፡፡ በዚህ ጊዜ በጥንቃቄ ወተቷን አልባ ልትሰጠው ይገባል፡፡

4. አልኮል የጡት ወተት ምርትን ከመቀነሱም በላይ የልጁን የነርቭ ዕድገት ሊያቀጭጭ ይችላል፡፡ ስለዚህ አቁሚ ባንልም የአልኮል መጠጧን ልትቀንስ ይገባል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ አልኮል ከወሰደች ልጇን ከሁለትና ሶስት ሳታት ቆይታ በኋላ ብታጠባው መልካም ነው፡፡

5. ሲጋራ የምታጨስ እናት ጡት አታጥቢ ማለት ቢከብድም ሲጋራ የሚያጨሱ አጥቢ እናቶች ጤነኛ መስለው ድንገት የሚሞቱ ህፃናት ሁኔታ ጋር የተያያዘ ነው፡፡ ስለዚህ ማጨስ ማቆም ለእርሷም ለልጇም መልካም ነው፡፡

6. አንዳንድ መድሃኒቶች፡፡ ይሄ መድሃኒቱን የሚያዘው የህክምና ባለሙያ የትኞቹን መድሃኒት ሲወስዱ ማጥባት እንደሚከለክል ይገልፅልሻል፡፡

ጡት ማጥባት መቼ ይቁም (Weaning)?

የአሜሪካ የህፃናት አካዳሚ (American Academy of pediatrics- AAP)  ለአንድ ዓመት ያህል ከተቻለም ከዚያ ቢያልፍ ጥሩነቱን መስክሯል፡፡ ስለዚህ መቼ ይቁም የሚለውን የእናትዬዋ ምርጫ ነው፡፡ ከቻለች ልጇ አቅመ አዳምና ሔዋንን እስኪርስ ማጥባት መብቷ ነው፡፡ ግን እንዴት ይቁም የሚለውን ትንሽ ነገር ማለት እፈልጋለሁ፡፡ ጡት ማጥባት ለማቆም ግራዋና ሬት መጠቀም በእኔ ይብቃ እላለሁ፡፡ እንደውም ጡቷ ጫፍ ላይ ፕላስተር ለጥፋ ልጇን አስደንግጣ ጡት ያስተወች ዘመድ አለችኝ፡፡ ስለዚህ እንዴት ይቁም? ድንገት ማቆም ለልጅም ዱብ ዕዳ ይሆንበታል፡፡ ለእናትየዋም ጥሩ አይሆንም፡፡ ለምሳሌ፣ እናትየው በጡት መወጠር እንዲሁም የወተት ትኩት ‹‹Milk fever›› ለተሰኘ መገለጫው ትኩሳት፣ ብርድ ብርድ ማለትና ደስ የማይል ስሜት ለሆነ በሽ ልትጋለጥ ትችላለች፡፡ ስለዚህ ማቆም ያሰበች እናት እንዲህ አድርጋ ልታቆም ትችላለች፡፡

1. ሲጀመር ህፃኑ ተጨማሪ ምግብ ሲጀምር ለጡት ያለው ፍላጎት እየቀነሰ ይመጣል፡፡

2. ለሁለት ወይም ለአምስት ቀን አንዴ ጡት መከልከል፡፡

3. የምታጠባበትን ደቂቃ ማሳጠር፡፡ ለምሳ ከ8-10 ደቂቃ በአንድ ጊዜ የምታጠባ ከሀነ ወደ 5 ወይም 3 ደቂቃ መቀነስ፡፡

4. የምታጠባበትን ጊዜ ማራራቅ፡፡ ለምሳሌ፣ በፊት በየሁለት ሰዓት የምታጠባ ከሆነ በየ 4 ሰዓቱ ማጥባት፡፡

5. ተጨማሪ ምግቡን ሌሎቹ የቤተሰቡ አባላት እንዲሰጡ ማድረግ፡፡ ከእናትም ውጭ ምግብ ሊሰጠው የሚችል አካል እንዳለ ማስለመድ፡፡ ህጻኑም ‹‹ለካም እንዲህ አለ!›› ማለት ይጀምራል፡፡ ይሄን ስል ግን እናትየዋ ሌላ ሀገር ትሂድ ማለቴ አይደለም፡፡ ስትርቀውም ደግሞ ሌላ ችግር ነው፡፡

6. ከጡት ወደ ጡጦ መሸጋገር ለህጻናት በመጀመሪያ ጊዜ ሞታቸው ነው፡፡ እርግጥ ከጡጦ ይልቅ በስኒ ቢጋቱ ተመራጭ ነው፡፡ እምቢ ካሉ ግን ጡጦውን መጠቀም ነው፡፡ ስለዚህ የጡጦውን ጫፍ ለህፃናቱ በሚሆናቸው መጠን መፈለግ ግድ ነው፡፡

በዚህ ጊዜ እናትየዋ ጡቷ እየተወጠረ ካስቸገራት ትንጥዬ ጨምቃ ልታፈስ ትችላለች፡፡ ብዙ ካለበችው ግን ወዲያውኑ መልሶ ይተካል፡፡ ከዚህ በተጨማሪ ቀዝቃዛ ነገር ለምሳሌ በረዶ ልታስቀምጥበት ትችላለች፡፡ ህመሙ በጣም የሚያስቸግራት ከሀነ ፓራሴታሞል ወይም አይቡፕሮፊን ልትጠቀም ትችላለች፡፡

በአጠቃላይ የእናት ጡት ወተት በዚህች ምድር ላይ ለህፃኑ የተዘጋጀ ምርጥ ስጦታ ነው፡፡ እናቶች አምጠው መውለድ ብቻ ሳይሆን ከመንታ ጡታቸውም አመንጭተው ህፃናቶቻቸውን ንጉስ ማድረግም ያውቁበታል፡፡ እናቶች ሆይ የመጀመሪያውን ስድስት ወሮች ለልጆቻችሁ የምግብ ምርጫ የራሳችሁ መንታ ምንጮች ይሁን፡፡

The post Health | መንታ ምንጮች | የእናት ጡት ወተት ለጤናማ ልጆች ዕድገት (ልዩ ዘገባ) appeared first on Zehabesha Amharic.

ብአዴን እና ሰዉ መሆን | ሸንቁጥ አየለ

$
0
0



ANDM 3

ሰዉ የሆነ ፖለቲከኛ በትንሹ ቢያንስ አንድ ቀን ሶስት ነገር እራሱን ይጠይቃል :- 1ኛ-የምሰራዉ ስራ ልክ ነዉ?

2ኛ -አጠገቤ ያሉ አለቆቼ የሚሰሩት ስራ ልክ ነዉ?
3ኛ-ህዝባችን ከእኔ ስራ እና ከአለቆቼ ስራ እየተጠቀመ ነዉ?

ሆኖም ብአዴን ዉስጥ ያሉ ፖለቲከኞች እንኳን ሶስቱን ጥያቄ አንዱንም ጥያቄ አይጠይቁም:: ጠይቀዉም አያዉቁም:: መጠየቅም አይፈልጉም::

እነሱ የሚጠይቁት አንድ ነገር ብቻ ነዉ:: “እንዴት ሆዴን መሙላት እችላለሁ? አለቆቼ ተበሳጭተዉ ከስራ እንዳያባርሩኝ እና ሆዴ እንዳይጎድል አለቆቼን እንዴት ማስደሰት እችላለሁ?”” በቃ:: ይሄዉ ነዉ:: ብአዴን ከሆንክ ከዚህ በላይ አትሄድም::

ሚሊዮን አማሮች ከምድረ ገጽ ተደመሰሱ ብትባል: አማራ ላይ የዘር ማጥፋት ሲጧጧፍ ብታይ ምንም የሚያስጨንቅህ ህሊና የለህም::ለምን ብለህ ለመጠየቅም ወኔ የለህም:: ብአዴን ከሆንክ ሆድህ እስካልጎደለ ድረስ ሁሉም ነገር ትክክል ሆኖ ነዉ የሚታይህ::

ስለሆነም ብአዴን እና ሰዉ መሆን የሚለያዩት አንድ ሰዉ ገና የብአዴን ፎርም ሲሞላ ነዉ::

ANDM

ከአራት እና ከሶስት አመት በፊት እንዲህ ሆነ:: በሽ የሚቆጠሩ ከጉራ ፋርዳ የተባረሩ አማሮች አዲስ አበባ ዉስጥ በየ መንገዱ ስለተበተኑ ጥቂት ነገር እንዲረዱ አንድ የርዳታ ማሰባሰቢያ ፕሮግራም አዘጋጅተን መንቀሳቀስ ጀመርን:: ከዚያም ብአዴኖች እንቅስቃሴአችንን ከፖለቲካ ጋር አገናኙት:: ከፖለቲካ ጋር ግንኙነት እንደሌለዉ አጥብቀን ገለጽን:: እኛን ለማስፈራራት ሞከሩ:: ሆኖም እኛ እርዳታ ማሰባሰቡን ማቆም አልቻልንም:: ወገን እየጠፋ ሌላ ማድረግ ባንችል ባለን አቅም መርዳት እንዳለብን ስለወሰንን ሰዎቹን ለመርዳት ሙከራ ማድረጋችችንን ቀጠልን:: በክርስቶስ ስም እዉነቱን ለመናገር እንቅስቃሴአችን ከፖለቲካ ጋር ምንም ግንኙነት አልነበረዉም::

ከዚያ ብኋላ ብአዴኖች ምን ቢያደርጉ ጥሩ ነዉ? ከቤቱ ተፈናቅሎ በጎዳና የተበተነዉን ህዝብ ማስፈራራት እና መዋሸት ጀመሩ:: “ነግረናችኋል እርዳታ ከነዚህ ሰዎች እንዳትቀበሉ:: እነሱ ተቃዋሚዎች ናቸዉ:: መንግስት ከተቃዋሚ እርዳታ የተቀበለን ሰዉ መልሶ አያሰፍርም:: አይረዳም: እኛ አሁን እናሰፍራችኋለን:: መንግስት ይረዳችኋል :: መንግስት ግን የሚረዳችሁ ከነዚህ ሰዎች /ከተቃዋሚዎች/ እርዳታ ካልተቀበላችሁ ነዉ::” እያሉ ማስፈራራት ጀመሩ::

እናም እንዲህ አድርገዉ ዋሽተዉ ሲያበቁ ተፈናቃዮቹን እንኳን ሊረዷቸዉ ሚኒሻሻ የሚባል እጅግ ሩቅና ጫካ የሆነ ወረዳ ዉስጥ ወስደዉ በተኗቸዉ:: እንዲራቡ:: እንዲሞቱ:: ወባ እንዲጨርሳቸዉ::በዚህ ወረዳ ዉስጥ እንኳን ምግብ ሊኖር የበሰበሰ በቆሎ እንኳን አልነበረም:: እናም ብዙዎቹ በረሃብ ሞቱ:: ህጻናት ወዲያዉ በወባ ሞቱ:: አንዳንድ ጉልበት ያላቸዉ ሰዎች እየጠፉ ከወረዳዉ አመለጡ:: በጣም የሚዘገንነዉ ደግሞ ከሚኒሻሻ ወረዳ ሰዎቹ እንዳያመልጡ ጠባቂ ሆነዉ የተመደቡት ብአዴኖች ነበሩ:: ከወረዳዉ ጠፍተዉ የመጡት ሰዎች እንዳብራሩልን ሊያመልጡ ሲሞክሩ በጥይት የተገደሉ ሰዎችም ሞልተዋል:: ይሄንንም የፈጸሙት ብአዴኖች ናቸዉ::

ይሄ ሁሉ የሚደረገዉ ከሰዉነት ተጠይቅ በተጣሉት ብአዴኖች ነዉ:: አማራ ላይ የዘር ማጥፋት ሲከናወን በፊታዉራሪነት የሚመራዉ ብአዴን የሚባለዉ አማራን እወክላለሁ የሚል ድርጅት ነዉ::

ANDM 2

ብአዴን እና ሰዉ መሆን መቼም ተገናኝተዉ አያዉቁም:: አሁን ደግሞ ህዝቡ በረሃብ እያለቀ እነሱ ይጨፍራሉ:: ሳያፍሩ ዉስኪ ይጠጣሉ:: ሳይፍሩ ስለ እድገት ይናገራሉ:: ብዙ ሚሊዮን ብሮችን ለምናምንቴ ድግስ ያባክናሉ::

እንዲህ አይነት ምንም ህሊና እና ወኔ የሌላቸዉ ፍጡራን እንዴት ተጠራርተዉ ሊሰባሰቡ እንደቻሉ አስገራሚ ነዉ::ወይም ደግሞ ህዉሃት በምን ጥበብ እንዲህ አይነት እምነተቢስ ሰዎችን በባትሪ ፈልጋ እንዳገኘቻቸዉ ያስደንቃል:: ህሊናና ወኔ ያለዉ ሰዉ እነዚህ ሰዎች መሃል ቢገባ በሶስተኛዉ ቀን ወይ ጨርቁን ጥሎ ይሄዳል ወይም ደግሞ አንድ አምስት አለቆቹን ገሎ እራሱን ያጠፋል::

ፕሮፌሰር ሰባስኪ የተባለዉ የጣሊያን ታሪክ ጸሀፊ ስለኢትዮጵያ ታሪክ ሲጽፍ እንዲህ ብሏል- ” ከሀበሻ ማህበረሰብ ዉስጥ ሁለት ጽንፈኛ ባህሪያት አሉ:: ይሄዉም ፍጹም የሆነዉን ጀግናም ሆነ ፍጹም የሆነዉን አድርባይም የምታገኘዉ ከሀበሻ ነዉ::”

እዉነት ነዉ ሀበሻን በትክክል ገልጾታል:: ወይ ፍጹም ጀግና ወይም ፍጹም አድርባይ ባህሪያት በደንብ ያሉበት ማህበረሰብ ነዉ::

ሰዉ ፍጹም አድርባይ ሲሆን ከሰዉነት ተጠይቅ ይወጣል:: ብአዴኖች ማለትም ይሄዉ ናቸዉ:: ሰዉነትና ብአዴን ተገናኝተዉ አያዉቁም::እንደሰዉ እራሳቸዉን ሆነዉ ለመቆም ብቃቱም: ወኔዉም ;: ህሊናዉም የላቸዉም:: ሆዳቸዉ ህሊናቸዉና ወኔአቸዉ ላይ ቆሞበታልና:: እንዲህ ሲሆን ሰዉ ከሰዉነቱ ይነጠላል::

The post ብአዴን እና ሰዉ መሆን | ሸንቁጥ አየለ appeared first on Zehabesha Amharic.

በሰሜን አሜሪካ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን የብአዴንን ባንዲራ እንዲህ ነበር ያቃጠሉት | Video

አርበኞች ግንቦት 7 ሕወሓት ታጋይ ክብሩ አሰፋን ረሸነው ሲል ከሰሰ

$
0
0

አርበኞች ግንቦት 7 በራድዮው አማካኝነት ባስተላለፈው መረጃ የሕወሓት መንግስት ታጋይ ክብሩ አሰፋን ረሸነው ሲል ከሰሰ:: የራዲዮው ዘገባ እንደሚከተለው እንደወረደ ተስተናግዷል::
kibru Assefa

ክብሩ አሰፋ ተወልዶ ያደገው በጎንደር-ታች አርማችሆ ማሰሮ ደንብ ነው፡፡ በሰላሳዎቹ መጀመሪያ ዕድሜ ላይ የሚገኘው ክብሩ አሰፋ የጀግኖቹ አርበኞች አታለል አሰፋና ክፈተው አሰፋ ታናሽ ወንድም ነው፡፡

ጀግናው አርበኛ አታለል አሰፋ በ1994 ዓ.ም ወደ በረሃ ወጥቶ የቀድሞውን የኢትዮጵያ ህዝብ አርበኞች ግንባር የተቀላቀለ ሲሆን በወልቃይትና በአርማጭሆ ለባንዳው የህወሓት ሰራዊት የእግር እሳት በመሆን መውጫና መግቢያ ነስቶታል፡፡

አርበኛ አታለል አሰፋ ከልቡ አርበኛ ነበር፤ አርበኛ አታለል አሰፋ እጅግ ጀግና ተዋጊ ነበር፤ አርበኛ አታለል አሰፋ ብልህ የጦር መሪና ጀግና አዋጊ ነበር፡፡

አርበኛ አታለል አሰፋ በደሙ ከፃፋቸው አስደማሚ የአርበኝነት ታሪኮቹ፣ አስደናቂ ጀግንነቱና አንፀባራቂ ጀብዱው መካከል 150 አርበኞችን እየመራ ተከዜን ተሻግሮ ሚያዚያ 16 1998 ዓ.ም አርማጭሆ ጎደቤ ላይ ሰፍሮ ይገኝ በነበረው የህወሓት መራሹ መከላከያ ሰራዊት ላይ ድንገተኛ ጥቃት ከፍቶ ጠንካራ ምት በማሳረፍ የጦር ሰፈሩን ሙሉ በሙሉ ደምስሶ በርካታ ቁጥር ያለው ወታደርና ዲሽቃ መማረኩ በግንባር ቀደምትነት ይጠቀሳል፡፡
atalel assefa

ጀግናው አርበኛ አታለል አሰፋ ለአራት ተከታታይ ቀናት የህወሓትን ሰራዊት አያራወጠ በእሳት አለንጋ በመግረፍ ሲፋለም ቆይቶ ሚያዚያ 20 1998 ዓ.ም ስናር ላይ በጀግንነት ወድቆ ውድና ክቡር ህይወቱን ለአገሩ ኢትዮጵያና ከጎኑ ተሰልፈው ይዋጉ ለነበሩት ለሚመራቸው 150 ጓዶቹ ሲል ከፈለ፡፡ ስሙ ከአርማጭሆ እስከ ወልቃይት ገኖ ተሰማ፤ ጀግንነቱ በስናርና ቋራ በረሃዎች አስተጋባ፤ የአርበኝነት ድምፁ በኤርትራ ምድረ በዳዎች ሁሉ ከፍ ብሎ አስገመገመ፡፡

አርበኛ ታጋይ ክፈተው አሰፋ፤ እሱም ጀግና ብቻ እንዲፈጥር ከታደለው አርበኛ አታለል አሰፋ ከወጣበት ማህፀን የበቀለ ነው፡፡ አርበኛ ታጋይ ክፈተው አሰፋ የቀድሞው የኢትዮጵያ ህዝብ አርበኞች ግንባር ከተመሰረተ ከአንድ ወር በኋላ በ1993 ዓ.ም በረሃ ወርዶ የአርበኝነቱን ጎራ ተቀላቀለ፡፡ አርበኛ ታጋይ ክፈተው አሰፋ 1995 ዓ.ም……. ዘመን መሪቅ ላይ ከባንዳው ህወሓት ሰራዊት ጋር በጀግንነት ሲፋለም እጁ ላይ በጥይት ተመትቷል፡፡ በተጨማሪም 1996 ዓ.ም አቡጢር ላይ አርበኝነትን ሲያፋፍም በድጋሜ እግሩ ላይ ተመትቶ ቆሰለ፡፡ ከዚያም በሱዳን ምድር ተጠልሎ ቁስሉን በመታከም ላይ እያለ የሱዳን ደህንነቶችና የፀጥታ ኃይሎች ለህወሓት አሳልፈው ሰጡት፡፡

አርበኛ ታጋይ ክፈተው አሰፋ ሰቆቃ እየተፈፀመበት በህወሓት ወህኒ ውስጥ ሲማቅቅ ለሦስት ዓመታት ከቆየ በኋላ በ2000 ዓ.ም ተመልሶ የአርበኝነት ትግሉን ተቀላቀለ፡፡ አርበኛ ታጋይ ክፈተው አሰፋ በእስር ባሳለፋቸው ሦስት ዓመታት ውስጥም የፖለቲካ እስረኞችን በህቡ በማደራጀት የጎንደሩን ግዙፍ ባህታ ወህኒ ቤት የመስበር ሙከራ አድርጓል፡፡ አርበኛ ታጋይ ክፈተው አሰፋ ዛሬም በአርበኝነት ሜዳ ላይ ይገኛል፡፡
kibru assefa 1

ክብሩ አሰፋ የእነዚህ ጀግኖች አርበኞች ታናሽ ወንድም በመሆኑ የህወሓት የበቀል በትር ገላው ላይ አረፈ፡፡ ክብሩ አሰፋ ወንድሞቹ ባካሄዱትና እያካሄዱት በሚገኙት አርበኝነት ምክንያት በበቀል ስሜት ብቻ በተነሳሳው ህወሓት በ2002 ዓ.ም በደህንነት ታፍኖ ወደ ወህኒ ተወረወረ፡፡ ሰቅጣጭ የምርመራ ድርጊትም ተፈፀመበት፡፡ ቀጥሎም የፈጠራ ክስ ተመስርቶበት የይስሙላሁ የህወሓት ፍርድ ቤት የ18 ዓመት አስር በየነበት፡፡ በመጨረሻም ክብሩ አሰፋ 6 የመከራ ዓመታትን በአሰቃቂ እስር ካሳለፈበት ወህኒ በነሀሴ ወር 2007 ዓ.ም ድንገት ተሰወረ፡፡ ወላጆቹ “ልጃችን ክብሩ የት ደረሰ?” በማለት የጎንደሩን ባህታ ወህኒ ቤት ቢጠይቁ “ሸዋ ሮቢት ሂዱና ፈልጉት” የሚል ምላሽ ተሰጣቸው፡፡ ጀግኖች አርበኞች አታለል አሰፋንና ክፈተው አሰፋን ከአብራካቸው ከፍለው ለኢትዮጵያ ህዝብ ነፃነት መሰዋእት ያቀረቡት የክብሩ አሰፋ ወላጆች ለሦስት ወራት ከአገር አገር እየተንከራተቱ የህወሓትን እስር ቤቶች አዳረሱ፡፡ ነገር ግን ልጃቸውን ክብሩን ፈፅሞ ሊያገኙት አልቻሉም፡፡

ክብሩ አሰፋ በነሀሴ ወር 2007 ዓ.ም እኩለ ሌሊት ላይ በህወሓት ደህንነቶች ከታሰረበት አዳራሽ እንደተወሰደ አብረውት የነበሩት ታሳሪዎች መስክረዋል፡፡ ህወሓት ከደርግ የከፋ ረሻኝና በቀለኛ ሆኗል፡፡

ጀግናው አርበኛ አታለል አሰፋ ለኢትዮጵያ ነፃነት ስናር ላይ በጀግንነት ወደቀ፡፡ አርበኛ ታጋይ ክፈተው አሰፋ እሱም እንደ ወንድሙ ለአገሩ ነፃነት ህይወቱን ሊከፍል ጦር ሜዳ ውስጥ ይገኛል፡፡ ክብሩ አሰፋን ህወሓት የበቀል ጥሙን ለማርካት ሲል ብቻ በግፍ ረሸነው፡፡ እናት ያለሀኪም እርዳታ ብቻዋን አምጣ ወልዳ ፍዳዋን ከፍላ ያሳደገቻቸውን ሦስት ወንድልጆቿን በባንዳው ህወሓት አጣች፡፡

The post አርበኞች ግንቦት 7 ሕወሓት ታጋይ ክብሩ አሰፋን ረሸነው ሲል ከሰሰ appeared first on Zehabesha Amharic.

ኃይሌ ገ/ስላሴ ለእኔ |ጌታቸው ሽፈራው

$
0
0

የስፖርተኞች ስም የተለጠፈበት ልብስ ለብሼ አላውቅም፡፡ ግን በስማቸው የታተመ ልብስ ብለብስላቸው ከማያሳፍሩኝ መካከል ኃይሌ አንዱ ነበር፡፡ ገና በልጅነቴ በሬድዮ የሀይሌን ማሸነፍ ሰምቼ ዘልያለሁ፣ ተሸነፈ ሲባል በጣም አዝኜ አውቃለሁ፡፡ እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ ለኃይሌ የተለየ ስሜት ነበረኝ፡፡ በቅርብ ግን ኃይሌ እየወረደብኝ መጣ፡፡ በቅርብ አመታት ኃይሌ ለምን ድሆችን (አካል ጉዳተኞችም፣ ህጻናትና አዛውንቶችን ጨምሮ) እንደማይረዳ ሲጠየቅ በተደጋጋሚ ‹‹ሰርተው ይብሉ!›› ሲል አዳምጬ ገርሞኛል፡፡ የሜቄዶንያው ቢኒያም ይህ የኃይሌ አባባል እንዴት ያናድደው?!
Haile_Gebrselassie_1
ከ3 አመት በፊት ግን የኃይሌ ስም ያረፈበትን ቲሸርት ብለብስ ኖሮ ይቆጨኝ እንደነበር የሚያስታውስ ነገር ሲናገር ሰማሁት፡፡ ‹‹ለምን ሰርተው አይበሉም!›› የሚለው ኃይሌ ሰርተውም የዋጋቸውን የማይከፈላቸው መምህራን ‹‹የስራ ዋጋችን ይከፈለን፣ ደመወዝ ይጨመርልን!›› የሚል ጥያቄ ሲያነሱ፣ እሱን የለመኑት ይመስል ይህን ጥያቄ ቅብጠት አድርጎ ሲወርፋቸው በሬዲዮ ሰማሁ፡፡ በሰይፉ ፕሮፍራም፡፡ ወቅቱ ኃይሌ ፕሬዝደንትነት ትልቅ ስልጣን መስሎት ‹‹ፕሬዝደንት›› ለመሆን የቋመጠበት ወቅት ነበር፡፡ መምህራን ደመወዝ ይጨመርልን ሲሉ መንግስት እንኳ እንዲህ የከፋ ዘለፋ አላወረደባቸውም፡፡

ያ ለመለስ ዜናዊ የተንሰቀሰቀው ኃይሌ፣ ለድሃ የሚራራ አንጀት የለውም፡፡ በዚህ ወቅት 15 ሚሊዮን ህዝብ ተራበ ቢባልም ‹‹ለምን ሰርተው አይበሉም!›› የሚል ይመስለኛል፡፡ እውነት ነው ኃይሌ የኢትዮጵያን ስም አስጠርቷል፡፡ በክፉ ቀን ስሟ ሲጠራ ግን መድረስ አይፈልግም፡፡ የእሱ ሜዳሊያ ሲያሸንፍ ለጨፈሩት፣ ሲሸነፍ ላለቀሱት አሁን ደግሞ ስቃይ ላይ ለሚገኙት ያመጣው ፋይዳው ያን ያህል ነው፡፡ በክፉ ቀን አለመድረሱ አንድ ነገር ሆኖ ቁስላቸው ላይ ጨው ለሚጨምርባቸው ደገሞ ሜዳሊያው ምንም ነው፡፡

እንደ ኢትዮጵያ ባለ በጭቆና ባለ ሀገር በተለይ ታዋቂ ሰዎች ልዩ ሚና ሊወጡ የግድ ነው፡፡ ለሚደግፋቸው ህዝብ የመኩላቸውን ሊወጡ ግዴታ አለባቸው፡፡ ያን ባያደርጉ እንኳ ዝምታ ከምንም ይሻላል፡፡ ከስርዓቱ ጋር ከቆሙ፣ ስርዓቱ በስንት ጊዜ አንዴ ‹‹ችግር›› ሲደርስበት እየተነፋረቁ እድሜ ልኩን እንዳይሰራ፣ ቢሰራም ለውጥ እንዳያመጣ በስርዓቶች የታሰረ ህዝብ ላይ ‹‹ለምን ሰርቶ አይበላም›› እያሉ ካላገጡ ክብርና ዝናቸውን መቀበል ይከብደኛል፡፡ ለእነ መለስ በአደባባይ እያለቀሰ፣ አደባባይ ላይ የወደቁትን አዛውንቶችና ህፃናት ‹‹ለምን አይሰሩም›› የሚለው ኃይሌም ለእኔ ክብሩን ንዷል፡፡ አሁን ድሮ በምናውቀው ሩጫው ሳይሆን የሥርዓቱ አሯሯጭም ሆኗል፡፡ ከስርዓቱ ጋር እየተሞዳሞዱ ባለሃብት በመሆን ከሆነ ህንዶችም፣ ቱርኮችም፣ ግብፆችም፣ ህወሓቶችም፣ ብአዴኖችም…..አሉ፡፡ በዚህ ኃይሌ የተለየ አይሆንም፡፡

በአጠቃላይ ኃይሌ ለህዝብ፣ ለክብሩ የሮጠ አይመስለኝም፡፡ እናም ጫማውን ቢሰቅል ባይሰቅል ጉዳዬ አይደለም፡፡ በሚቀጥለው አመት ተመልሻለሁ ብሎ ሪኮርድ ቢሰብር፣ ቢያሸንፍ፣ በታዕምር በ90፣ በ103…..አመቱ ቢሮጥ….ከማጨብጨቤ በፊት የሚታየኝ እሱ ለኢትዮጵያውያን ሳይሆን ለጨቋኝ ስርዓት አጨብጫቢ መሆኑ ነው፡፡ የሚታወሰኝ በህዝብ ላይ የሚቀልድ፣ ለስርዓቱ እንባ፣ ለህዝብ የአዞ እንባ እንዳለው ነው፡፡ እናም ኃይሌን፣ ለማስታወስ፣ ለማድነቅም……ኃይሉም ሞራሉም የለኝም፡

The post ኃይሌ ገ/ስላሴ ለእኔ | ጌታቸው ሽፈራው appeared first on Zehabesha Amharic.

Viewing all 15006 articles
Browse latest View live