Quantcast
Channel: Ethiopian News | ዘ-ሐበሻ | Latest News Provider | News For All
Viewing all 15006 articles
Browse latest View live

ለአቡነ ጳውሎስ የመቃብር የነሐስ ሐውልት የተመደበው 1.5 ሚልዮን ብር ነው

$
0
0

የአቡነ ጳውሎስ ሙት ዓመት ትናንት ታስቦ ውሏል። ይህን ተከትሎ በወጡ መረጃዎች የሟቹን ፓትርያርክ የመቃብር ሐውልት በነሐስ ለማሠራት 1.5 ሚልዮን ብር የተመደበ መሆኑ ታውቋል። የሐራ ሙሉ ዘገባ እንደወረደ ይኸው፦
ለሐውልቱ ሥራ የተዋዋለው ተቋራጭ አድራሻውን አጥፍቶ ጀርመን ከረመ
በውሉ መሠረት ከነሐስ የሚሠራውን ሐውልት በ186 ቀን ሠርቶ ማስረከብ ነበረበት
ለጥቅምት ፲፪ ቀን ፳፻፮ ዓ.ም ‹‹ዝክረ አበው›› እንዲያደርስ ታዝዟል

ነሐሴ ፲ ቀን ፳፻፬ ዓ.ም ሌሊት ከዚህ ዓለም በሞተ ሥጋ የተለዩት የአምስተኛው ፓትርያሪክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ ኅልፈት አንደኛ ዓመት መታሰቢያ ሥነ ሥርዐት በዛሬው ዕለት በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል በማሕሌት፣ በጸሎተ ፍትሐትና በቅዳሴ ታስቦ ውሏል፡፡

abunapauolos(1)በቤተ ክርስቲያናችን የሙታን መታሰቢያ ቀኖና መሠረት በዐጸደ ነፍስ ያሉትን ዕጣን፣ ጧፍ እና መሥዋዕት በማቅረብ ተዝካረ ጸሎት ማድረግ ሥርዐት መኾኑን ከመጽሐፈ ግንዘት እና መጽሐፈ ሢራክ በመጥቀስ ያስረዱት ብፁዕ አቡነ ገሪማ፣ የአቡነ ጳውሎስ ዕረፍት አንደኛ ዓመት መታሰቢያ የሚካሄደው ‹‹ቅዱስነታቸው በሁሉም አቅጣጫ ያስመዘገቧቸውን የሥራ ውጤቶች በማዘከር›› መኾኑን ገልጸዋል፡፡

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ከዐሥራ አንድ ያህል ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት ጋራ የሙት ዓመት መታሰቢያ ሥነ ሥርዐቱን መርተዋል፤ ንግግራቸውም ‹‹ነፍሰ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ወፓትርያሪክ አባ ጳውሎስን ከማኅበረ መላእክት፣ ከማኅበረ ጻድቃን እንድትደምርልን እንለምንሃለን›› በሚል የተወሰነና የተጠቃለለ ነበር፡፡

ጸሎተ ፍትሐቱ በተከናወነበት የካቴድራሉ ዐጸድ ውስጥ የሚገኘውና ሥራው ያልተጠናቀቀው መካነ መቃብራቸው በእብነ በረድ ተዘግቷል፤ በቆርቆሮ የታጠረው ዐጸድ ዙሪያው ጒንጒን አበባ ተደርጎበት የቀድሞውን ፓትርያሪክ ግዙፍ ምስል በያዘ ባነር ተሸፍኗል፤ ‹‹መልካሙን ገድል ተጋድያለኹ. . .›› የሚለው የቅዱስ ጳውሎስ ጥቅስ በታላላቅ ፊደላት ሰፍሮበታል፡፡ የመታሰቢያ ሥነ ሥርዐቱ ተካፋዮች ከጸሎተ ፍትሐቱ በኋላ ወደተቀጸረው የመካነ መቃብሩ ዐጸድ ቢዘልቁም ከዚህ በቀር የሚያዩት ነገር አልነበረም፡፡

የመቃብር ሐውልቱ ሥራ ስለመዘግየቱ የተመለከቱ ጥያቄዎችና ቅሬታዎች ለመንበረ ፓትርያሪክ ጠቅላይ ቤተ ክህነቱ መድረሳቸውን የገለጹት የጽ/ቤቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ ብፁዕ አቡነ ማቴዎስ፣ ሐውልቱ ከነሐስ እንዲሠራ ተወስኖ ሥራውን ለማስፈጸም የተቋቋመው ኮሚቴ ለክንውኑ በተመደበው ገንዘብ መሠረት ጨረታ አውጥቶ ለአሸናፊው ተቋራጭ ውል ተሰጥቶ እንደነበር አስታውሰዋል፡፡

‹‹በጨረታው ውል መሠረት ተቋራጩ ሥራውን በ186 ቀን ጨርሶ ማስረከብ ነበረበት፤ ባለማጠናቀቁ ለመንፈቅ እንዲያደርስ ተራዘመለት፤ አላደረሰም›› ያሉት ብፁዕነታቸው፣ ‹‹ስልኩንም አጥፍቶ ነሐሴ 6 ቀን ብቅ ብሎ ጀርመን ነበርኹ ብሎ አረዳን›› ሲሉ እርሱ እየተጠበቀ ሥራው ከውሉ ውጭ እስከ ሙት ዓመት ድረስ መዘግየቱን አስረድተዋል፡፡

ብፁዕ አቡነ ማቴዎስ ለሐውልቱ ሥራ የተመደበው ገንዘብ [1.5 ሚልዮን ብር መኾኑ ተዘግቧል] በባንክ ተጠብቆ እንዳለ መኾኑን ገልጠው÷ ‹‹እብነ በረዱ ተስተካክሎ ተቀምጧል፤ ተቋራጩም ነሐሱን [ከነሐስ የተሠራ ምስላቸውን] አምጥቼ ማቆም ብቻ ነው የሚቀረው ብሎናል፤ በተገባው ውል መሠረት ለጥቅምት ቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት ባሉበት ይመረቃል፤ የዘገየው በእኛ ምክንያት አይደለም፤ ይህን እንድትረዱልን ነው፤›› ሲሉ ምላሽ ሰጥተዋል፡፡

በቀድሞው ዘመነ ፕትርክና ይኹን አሁን የፓትርያሪኩ ልዩ ጽ/ቤት ሓላፊ የኾኑት ብፁዕ አቡነ ገሪማ በንባብ ባሰሙት ዝክረ ፓትርያሪክ አቡነ ጳውሎስ፣ ‹‹በዘመናቸው 49 ኤጲስ ቆጶሳትን አስገኝተዋል›› ብለዋል፡፡ ለአንደኛ ዓመት መታሰቢያ በብፁዕነታቸው ተዘጋጅቶ በሥነ ሥርዐቱ ላይ የተሠራጨውና የፓትርያሪኩን ዜና ሕይወትና ሥራዎች የያዘው ኅትመትም የአቡነ ጳውሎስን ኅልፈት አስመልክቶ የሚከተለውን አስፍሯል፤

ይኹንና ‹‹መኑ ሰብእ ዘየሐዩ ወኢይሬእያ ለሞት፤ ሕያው ሁኖ የሚኖር ሞትንስ የማያይ ሰው ማን ነው?›› /መዝ.88÷48/ ተብሎ በነቢየ እግዚአብሔር ዳዊት በተነገረው መሠረት ቅዱስ ፓትርያርካችን በጾመ ፍልሰታ ለማርያም በመንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም ቤተ ክርስቲያን በመቀደስና ሐዋርያዊ ተልእኮ በመፈጸም አንደኛውን ሱባኤ ካጠናቀቁ በኋላ ነሐሴ 8 ቀን 2004 ዓ.ም በዐሥራ አንድ ሰዓት አካባቢ ለምርመራ ወደ ሆስፒታል ሄደው በመታከም ላይ እንዳሉ ነሐሴ 10 ቀን 2004 ዓ.ም ከንጋቱ 11፡00 በተወለዱ በ76 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም በሞተ ሥጋ ተለይተዋል፡፡

ለረጅም ጊዜ የአቡነ ጳውሎስ መጋቤ ሥርዐት ኾነው ያገለገሉት ፕሮቶኮል ሹማቸው ሙሉጌታ በቀለ ስለ ጤንነት ይዞታቸውና ድንገተኛ ኅልፈታቸው ነሐሴ ፲፪ ቀን ፳፻፬ ዓ.ም በፓትርያሪኩ የቀብር ሥነ ሥርዐት አፈጻጸም ሂደት ላይ ተወያይቶ መርሐ ግብር ለማውጣት ተሰብስቦ በነበረው የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ ፊት ቀርበው እንደሰጡት የተነገረው የቃል አስረጅ ደግሞ ፓትርያሪኩ ከተባለው ሰዓት ቀደም ብለው ስለማረፋቸው የሚጠቁም ነው፤

ማክሰኞ [ነሐሴ 8 ቀን] በቅድስት ማርያም አስቀድሰው ነበር፤ ከቅዳሴ ከወጡ በኋላ ከተወሰኑ አባቶችና እንግዶች ጋራ ምሳ በሉ፤ እኔም ወደ ቤቴ ሄድኩ፤ ማምሻውን አመማቸው ተባለና ተጠርቼ መጣኹ፤ ጤንነታቸውን በግል የሚከታተለው ዶ/ር ተጠርቶ መጣና አያቸው፤ ለክፉ የሚሰጥ አይደለም ብሎ ሄደ፤ ነገር ግን ሕመም ስለጠናባቸው ብዙ ጊዜ ወደሚታከሙበት ባልቻ ሆስፒታል ይዣቸው ሄድኹ፤ ሐኪሞቹ ሲመረምሯቸው ሳምባቸው ውኃ ቋጥሯል፤ ፈቃድዎ ከኾነ ውኃውን እንቅዳው ብለዋቸው ኦፕሬሽን ክፍል ገብተው ተቀዱ፤ ረቡዕ ተሽሏቸው ሰውም ሲያናግሩ ውለው ነበር፤ እኩለ ሌሊት ገደማ ግን ተጫጫነኝ ሲሉኝ ተረኛ ዶክተሮችን ጠርቼ አዩዋቸው፤ ዕረፍት እንዲያደርጉ አዘዟቸው፤ እኔም ከጎን ወደነበረ ማረፊያ ክፍል ሄድኩ፤ ንጋት ላይ ወደ ክፍላቸው ስመለስ ዐርፈው አገኘኋቸው፡፡

በወቅቱ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ የነበሩት ብፁዕ አቡነ ሕዝቅኤል ለአሜሪካ ድምፅ ሬዲዮ የአማርኛ ቋንቋ አገልግሎት ሲናገሩ፣ ‹‹አብረን አስቀድሰን ቢሮም አብረን ቆይተን ነበር፤ ፓትርያሪኩ በስኳር ሕመም ይታወቁ ነበር፤ ጾሙም ሕመማቸውን ሳያከፋው አልቀረም፤ ብቻ ታመው አቅኑኝ ሳይሉ ፃዕር ጋዕር ሳይበዛባቸው ቅዳሴውን ሳያቋርጡ ከቤተ ክርስቲያን ወደ ቤተ ክርስቲያን ነው የሄዱት፤›› ብለው ነበር፡፡

ሌሎች ምንጮች በበኩላቸው የፓትርያሪኩን ሕመም ያከፋው÷ በወቅቱ ይፋ ያልተደረገውን የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር ኅልፈት ሲረዱ በደረሰባቸው ከፍተኛ ድንጋጤና ይህን ተከትሎ ይወስዷቸው የነበሩትን መድኃኒቶች አወሳሰድ ማስተጓጎላቸው ያስከተለባቸው ‘multiple organ failure’ እንደነበረ ሲናገሩ ቆይተዋል፡፡

የፓትርያሪክ አቡነ ጳውሎስ ቤተ ዘመዶች ‹‹የአቡነ ጳውሎስ ፋውንዴሽን›› ለማቋቋም መንቀሳቀስ መጀመራቸው ከመንበረ ፓትርያሪኩ ምንጮች ተሰምቷል፡፡ ይህ ፋውንዴሽን በፓትርያሪኩ ፳ኛ ዓመት በዓለ ሢመት በሼራተን አዲስ በተከበረበት ወቅት ራእይ ለትውልድ የተሰኘው አካል በስማቸው ‹‹የካንሰር፣ቲቢና ኤድስ የሕክምናና ማገገሚያ ማእከል›› በ200 ሚልዮን ብር ለመገንባት ካቀደበት የበዓለ ሢመት ስጦታ ጋራ ግንኙነት ይኖረው እንደኾነ አልታወቀም፡፡

የፓትርያሪኩ ኅልፈት በተሰማበት ዕለት ረፋድ መኖርያ ቤታቸው፣ በስጦታ ያገኟቸው አይከኖች፣ መስቀሎች፣ አልባሳትና ሽልማቶች የሚገኙበት ሙዝየም ፖሊስና የጠቅላይ ቤተ ክህነቱ ጠቅላላ አገልግሎት በተገኘበት መታሸጉ ተገልጦ የነበረ ቢኾንም ከአሮጌ አልጋና ካገለገሉ አልባሳት በቀር የተገኘ ነገር አለመኖሩ ተጠቁሟል፤ በምትኩ ፓትርያሪኩ በሽልማት ያገኟቸው አራት መኪኖች የይገባናል ጥያቄ እንደቀረበባቸውና ለዚህም ክሥ እንደሚመሠረት ተሰምቷል፡፡

ቢያንስ ቅዱስ ሲኖዶስ በግንቦት ፳፻፭ ዓ.ም የርክበ ካህናት ምልአተ ጉባኤው በቀድሞው ፓትርያሪክ ንብረት ላይ ለመወሰን የያዘው አጀንዳም በቂ ውይይት እንዳልተካሄደበትና ውሳኔም እንዳልተሰጠበት ነው ለመረዳት የተቻለው፡፡ በ፲፱፻፺፩ ዓ.ም ሕገ ቤተ ክርስቲያን አንቀጽ ፵፭ ንኡስ አንቀጽ (፩) እና (፪) ‹‹ስለ ቅዱስ ሲኖዶስ አባላት ሀብትና ንብረት›› ግን የሚከተለው ተደንግጓል፤

አንድ የቅዱስ ሲኖዶስ አባል ከዚህ ዓለም በሞት በሚለይበት ጊዜ የግል የኾነ ገንዘብ ቢኖረው ይረዳቸው ለነበሩ ዕጓለሙታንና ችግረኞች ይሰጣል፡፡ (አብጥሊስ ፴፱)
ኤጲስ ቆጶሱ መንፈሳዊ አገልግሎቱን ሲያከናውንባቸው የቆዩ መጻሕፍት፣ አልባሳት፣ አርዌ ብርት፣ መስቀሎች፣ መቋሚያዎችና የመሳሰሉት ሁሉ በቤተ ክርስቲያኒቱ ንብረትነት በስሙ ተመዝግበው በሀገረ ስብከቱ በሙዝየም ይቀመጣሉ፡፡
ነገር ግን እንደ ሕጉ አልኾነም፤ እንዲኾንም ተከታትሎ የሚጠይቅና የሚያስፈጽም አካል ያለ አይመስልም፡፡ እንዲያውም የታዛቢዎች አስተያየት የሚያስረዳው የቀድሞው ፓትርያሪክ ዜና ኅልፈት ከተሰማበት ዕለትና ከዚያም በኋላ የአንዳንድ ጉዳዮች አያያዝ፣ ‹‹ሲደከምበትና በብርቱ ሲፈለግ የቆየው የአቡነ ጳውሎስ ኅልፈት ብቻ እንደነበረና ሁሉም ነገር ከኅልፈታቸው ጋራ አብሮ ያከተመ የሚያስመስል ነው፡፡››


ዓባይ ሊያለማን ወይስ ሊያጠፋን? –የሕዳሴው ግድብና ዐባይ፣ የሚሊኒየሙ ዐባይ ተጋቦት

$
0
0

አዘጋጅ ለኢትዮጵያ ፍቅር ከቃሊቲ

የዐባይ ሥረ_መሠረትና የሕዳሴው ግድብ ማነጣጠሪያ እነሆ!
ጥናቱ የተፈጸመው ሚያዚያ 2003 (2011 እ ኤ አ) ነው። አቅርቦት የፀሐፊው ትክክለኛ ቅጂ (በአቀራረባዊ ጥንቅር) መነሻ የጊዜው የኢትዮጵያ ጉዳይ ሆኖ የቀጠለውና ሕዝቡም የጠየቁትን እያደረገ ያለበት የሚሌኒየሙ ታላቅ የዐባይ ግድብ እንደተነገረው፤ የሚገደበው ከሱዳን ድንበር 17 (አሥራ ሰባት) ኪሎሜትር ባለ ቀረቤታ በዐባይ ወንዝ ላይ ነው። ግድቡ ወደ 62 ቢሊዮን ሜትር ኩብ ውኃ የመያዝ አቅም አለው። የውኃው መጠን የጣና ሐይቅ ከሚይዘው ውኃ እጥፍ ይሆናል።
በሚታቆረው ውኃ 6ሺ (ስድስት ሺ) ሜጋ ዋት የኤሌትሪክ ኃይል ሊመረት ታቅዷል። የሚመረተው የኤሌክትሪክ ኃይል ለኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን ለሱዳንና ለግብፅም ሊሸጥ ታስቧል። ይህ ግንባታ 80
ቢሊዮን ብር ይፈልጋል።
Blue Nile
ገንዘቡ በግብፅ ተፅዕኖ ሳቢያ የውጭ ብድር ወይም ዕርዳታ እንዳያገኝ ስለተደረገ፤ በኢትዮጵያ ሕዝብ የመዋጮና ቦንድ ሺያጭ ሊሸፈን ተወስኗል።ለሕዝቡም ታሪካዊ ተዐምር ሊሠራ እንደሆነና የልማት
ሁሉ አንጋፋ እንደሆነ ተነግሮት የቻለውንና ያልቻለውንም ከማድረጉ በላይ ለሃገር የሚበጅ ልማታዊ ድንቅ እንደተፈጠረ ተበስሮለታል። ባለፈው ሚያዚያ (April) 2013 እ ኤ አ
ወር ማብቃያ አካባቢ በወጣው ዜና ደግሞ (ይህ ጥንቅር ከቀረበ ከሁለት ዓመት በኋላ መሆኑ ነው። ቻይና ለሚሌኒየሙ ግድብ ግንባታ 1.5 ቢሊዮን ዶላር ልታበድር ነው ተብሏል።
ታዲያ ግብፅና ሱዳን ምነው ዝም አሉ?
እኮ ቢጠቅማቸውማ ነው ዝምታቸው፤ የዐባይ ልጅ ይህ እንዴት ያየዋል? አባይ (ናይል)እየተባለ የሚጠራው በዓለም ረዥሙ ወንዝ፣6671 ኪሎ ሜትር እርዝማት ሲኖረው፣ከዘጠኝ አገሮች ይመነጫል።ግብፅ ምንም የምታመነጨው የውኃ አስተዋፆ የላትም። ሆኖም በናይል ውኃ በከፍተኛ ደረጃ ተጠቃሚ አገር ናት። ግብፅ 100% የሰሐራ በረሃ አካል በመሆኗ በሜዲቴሪንያን አካባቢ ጥቂት ዝናብ ጠብ ከማለቱ ሌላ ከዓመት ዓመት ዝናብ አይጥልም።
በሌላ በኩል ደግሞ ከሁሉም የናይል ተፋሰስ አገሮች ይበልጥ የ80% በመቶ ከአባይና ከሌሎች የኢትዮጵያ ወንዞች የሚገኘው ውኃ አባይን ይገልጸዋል። በጠቅላላው የናይል ወንዝ 74 ቢሊዮን
ሜትር ኩብ ውኃ በዓመት ሲሰጥ ከዚህ ውስጥ ከኢትዮጵያ የሚገኘው የውኃ ድርሻ መጠን 54 ቢሊዮን ሜትር ኩብ ውኃ ነው። የዚህ ሁሉ ውኃ ምንጭ ኢትዮጵያ ስትሆን፤እንደ ሱዳንና ግብፅ እምነት ጥቂት ውኃ እንኳን ለመጠቀም መብት የላትም።ሌሎቹንም የናይል ውኃ አመንጪና ባለቤት የራስጌ አገሮችን በማግለል መብታቸውን ገፍፈው ሱዳንና ግብፅ ተከፋፍለውታል።
እ ኤ አ 1959 ዓ ም በተፈራረሙት ስምምነት መሠረት ግብፅ 55.5 ቢሊዮን ሜትር ኩብ ፤ሱዳን ደግሞ 18.5 ቢሊዮን ሜትር ኩብ ውኃ ይወስዳሉ።በተለይ ግብፅ የውኃው ዋና ባለቤት እራሷን አድርጋ በመቁጠር አመንጪዎቹን የራስጌ አገሮች ለአነስተኛ የውኃ ጠቀሜታ እንኳን ፈቃጅ መሆን አለብኝ ባይ ናት። ለዚህም ኢትዮጵያን ማዳከም ወይንም ማጥፋት ተልዕኮዋ ሆኗል።
የአባይ ጠቀሜታ
ግብፅና ሱዳን ፍፁም ተጠቃሚዎች ሲሆኑ፤ በተቃራኒው የውኃ መነሻ የሆነችው ኢትዮጵያ ተጠቃሚ አልሆነችም። ግብፅ 3.0 ሚሊዮን ሄክታር መሬት በመስኖ ታለማለች። ሱዳን 1.8 ሚሊዮን ሄክታር እንደዚሁ በናይል መስኖ ታለማለች። ኢትዮጵያ አትጠቀምም በመስኖ አለማችም። የግብፅ በረሃ በናይል ውኃ በሺ ዓመታት የሚቆጠር የመስኖ እርሻ ልምድ ለምቶ እራሳቸውን ከመመገብ አልፈው የዳበረ ኢኮኖሚ ገንብተውበታል። አባይን ወደ ምዕራብ የግብፅ በረሃ ቀይሰው በመውሰድ ተጨማሪ 1.2 ሚሊዮን ሄክታር በረሃ ለማልማት መንቀሳቀስ ከጀመሩ ቆይተዋል።በዚህ ምዕራባዊ ከተማ ከአንድ ሚሊዮን ሕዝብ በላይ የሚኖርበት ዘመናዊ ከተማ እየተገነባ ነው። የሲናይንም በረሃ ለማልማት በዓመት 4.5 ቢሊዮን ሜትር ኩብ የአባይ ውኃ የሚያስተላልፍ ቧንቧ ዘርግተዋል። የመስኖ ሥራቸውን ለማካሄድ ያስቻላቸውም ታላቁ የአሳዋን ግድብ ነው።ግድቡ 162 ቢሊዮን ሜትር ኩብ ውኃ የማከማቸት አቅም አለው። በክረምት ወራት ከኢትዮጵያ የሚፈሰውን ውኃ አጠራቅመው በመያዝ በሰከንድ 1500 ቶን ውኃ እየለቀቀ በረሃውን ያለማል። ይህም ሆኖ በግብፆች ዕቅድ ተጨማሪ በረሃ ለማልማት 15ቢሊዮን ሜትር ኩብ ውኃ ተጨማሪ ያስፈልገዋል። ለዚህም የተለያዩ
ፕሮጀክቶች አስጠንተዋል። ጥናቱ ተጠናቆ ግንባታውም ተጀምሮ የነበረው አንዱ ፕሮጀክት በደቡብ ሱዳን ክልል ያለው የጀንገሌ ካናል ፕሮጀክት ነበር። የናይል ወንዝ በደቡብ ሱዳን ሱድ እየተባለ
የሚጠራውን ረባዳና ረግረግ ሰፊ መሬት አቋርጦ ያልፍል።ወንዙ በክረምት ከአፍ እስከ ገደብ ሲሞላ ግደቡን ጥሶ ለጥ ወዳለው ሜዳ መፍሰስ ይጀምራል።ግድቡን አልፎ የተንጣለለው ውኃ ተመልሶ ወደ ወንዙ ሊገባ ስለማይችል፤እንደተንጣለለ ይደርቃል።ይህም በፀሐይ ሙቀት እየተነነ ይጠፋል። ታዲያ ግብፃውያን የጀንግሌ ካናልን ፕሮጀክት ያጠኑትና ሥራውንም የጀመሩት በትነት የሚባክነውን ውኃ
በማግኘት የናይልን ውኃ መጠን 10% ከፍ ለማድረግ ነበር።
1ኛ የጀንግሌ ካናሉ ግንባታ የተጀመረው የደቡብ ሱዳን ነፃ አውጪ ድርጅት የነፃነት እንቅስቃሴ በጀመረበት ወቅት ስለነበር ፕሮጀክቱ ሳይገፋ አገራችን ይደርቃል፣ ኢኮሎጂውም ይለወጣል፣ በማለት
ኤስ .ፒ .ኤል. ኤም ፕሮጀክቱ ላይ ጥቃት በመሰንዘር አጨናገፈው።
2ኛ ተጨማሪ ውኃ ለማግኘት ያስችላል ተብሎ የተጠናው ሌላው ፕሮጀክት ደግሞ በኢትዮጵያ ትልልቅ ግድቦች መገንባትና የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጨት ነው። ግብፅ በረሃማ አገር በመሆኗ የፀሐይ
ሙቀት ያጠቃታል፤በዚያ የተነሣ በአገራቸው ከተገነባው ቃላቁ የአስዋን ግድብ በፀሐይ ሙቀት ብቻ በትነት ከተከማቸው ውኃ 12% ይባክናል።ይህ በጣም የሚያሳስባቸው ጉዳይ ነው። ብዙ ውኃ ሊይዝ የሚችል ሌላ ትልቅ ግድብ ለመገንባት የሚቻለበት ቦታ ስለሌላቸው ተጨማሪ ውኃ በሃገራቸው ውስጥ ለማከማቸት ያላቸው ዕድል በጣም የመነመነ መሆኑን ተረዱት። በዚህ የተነሣ ጥረታቸውን በኢትዮጵያ ላይ አድርገዋል።በደጋው ኢትዮጵያ ትላልቅ ግድቦች ለገነቡባቸው የሚችሉበት ቦታዎች በርካታ ናቸው። በሚገደቡት ግድቦች የሚከማቸው ውኃ በትነት የመባከን አደጋ አያጋጥመውም።ውኃው ሳይባክን ለብዙ ጊዜ ተጠብቆ የመቆየት ዕድል አለው።ኤሌክትሪክ ለማምረት እየተባለ ከሚገነቡት ግድቦች ከሚለቀቀው ውኃ ምን ያህል ተጨማሪ ውኃ ሊገኝ እንደሚችል ግብፃውያን አስጠንተው ውቀውታል።
በጥናቱ መሠረት በኢትዮጵያ 23 ትላልቅ ግድቦችን በአባይ መጋቢ ወንዞች ላይ መገንባት የሚቻልባቸው ቦታዎች ተለይተው ታውቀዋል፤መነሻ ጥናት ተካሄዶባቸዋል፤እንደጥናቱ በእነዚህ ቦቻዎች በሚገነቡ ግድቦች ብዙ ቢሊዮን ሜትር ኩብ መጠን ያለው ውኃ ይከማቻል።ከዚያም በያንዳንዱ ግድብ የሚተከሉት የኤሌክትሪክ ማመንጫ ተርባይን ለማሽከርከር ውኃ ይለቀቃል።የአባይ ወንዝ በሚሞላበት ወቅት የአገራችንን ድንበር አልፎ ሱዳን ሲገባ የሚያፈሰው የውኃ መጠን 400 ሜትር ኩብ ውኃ በሰኮንድ ሲሆን አባይ ደረቀ በሚባልበት በበጋው ወቅት ደግሞ 4 ሜትር ኩብ ውኃ በሰኮንድ ይፈሳል።
ልዩነቱን አጢኑት በበጋው የሚፈሰው በአንድ መቶ ጊዜ ይቀንሳል።ከዚህ ሁኔታ መገንዘብ የሚቻለው በሱዳንም ሆነ በግብፅ በክረምት ወራት ከኢትዮጵያ የሚፈስላቸውን ውኃ ገድበው በመያዝ በበጋ ወራት እየለቀቁ መጠነኛ የእርሻ ሥራ ከማካሄድ ውጭ የመስኖ እርሻ እንቅስቃሴ አያካሄዱም ማለት ነው። በኢትዮጵያ ግድቦች ተገንብተው ውኃ እየለቀቁ ተርባይኖችን ማሽከርከር ሰንጀምር ግን ይህ
ሁኔታ ሙሉ በሙሉ ይለወጣል። ከተጠኑት 23 የግድብ ሥፍራዎች ውስጥ አነስተኛ ውኃ የማከማቸት አቅም ያላቸው አራት ግድቦች ቢገነቡና በየአንዳንዱ ግድብ ኤሌክትሪክ ለማመንጨት፤ አራት አራት
ተርባይኖች ቢተከሉና እነዚህን ተርባይኖች ለማሽከርከር 20 ሜትር ኩብ ውኃ በሰኮንድ ቢለቀቅ ሱዳንና ግብፅን አባይ ሲደርቅ 80 ሜትር ኩብ ውኃ በሰኮንድ ያገኛሉ ማለት ነው።
ኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ብቻ ለማምረት ፈልጋ ግድብ ከገደበችና ተርባይኖችን ለማሽከርከር አንድ ጊዜ ውኃ መልቀቅ ከጀመረች በኋላ ውኃውን በከፊል ወይም በሙሉ ለመስኖ እርሻ ልማት መጠቀም
ብትሞክር የሱዳንና የግብፅን ሕዝቦች በረሃብ ፈጀች፤ የአባይን አቅጣጫ ቀየረች፤ በሚል ሰበብ ለጦርነት መነሳታቸው አይቀርም። በዓለም አቀፍ ደረጃም እንድትወገዝ ፓለቲካዊና ኤኮኖሚያዊ ጫና
እንዲወድቅባት ያደርጋሉ።
በዚህ ምክንያት በአባይ ወይም በአባይ ገባር ወንዞች ላይ ግድብ ገንብተን የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጨት ከመጀመራችን በፊት ውሎ አድሮ ኢትዮጵያን የሚጎዳ ሁኔታ አለመፍጠሩን ከብዙ አቅጣጫዎች መመርመር አለብን። እንደሚታወቀው የኤሌክትሪክ ኃይል ለማንኛውም አገር ዕድገትና ሥልጣኔ ወሳኝ ኃይል ነው። ኃይል እንደመሆኑ ሁሉ ኢትዮጵያም የኢሌክትሪክ ኃይል በከፍተኛ ደረጃ ያስፈልጋታል። በቀላል መንገድ የኤሌክትሪክ ኃይል ለማግኘት ደግሞ ያላትን የውኃ ኃይል መጠቀም ይኖርባታል። በውኃው ኃይል ኤሌክትሪክ ስናመርት ግን ተርባይኖቹን የሚያሽከረክረው ውኃ ተለቆ የሚሄድ ሳይሆን ለመስኖ ልማት ላይ መዋል ይኖርበታል።ግድብ ፣ገድበን ኤሌክትሪክ ለማመንጨት ስናስብ፣ የሚለቀቀው ውኃ እታች ወርዶ ማሳውን እንዲያጠጣ ተደርጎ መታቀድ ይኖርበታል።በዚህ አኳኋን ካልታቀደ በከፍተኛ ወጪ ያጠራቀምነውን ውኃ ያለምንም ክፍያ ለሱዳንና ለግብፅ አሳለፈን ሰጠን ማለት ነው። ከዚህ ግንዛቤ በመነሣት በደርግ ጊዜ የመልካ ዋከና የኤሌክትሪክ ማመንጫ ጣቢያ ሲገነባ በተጓዳኝ በኡጋዴን ጎዴ አካባቢ ተርባይኑን ለማሽከርከር የሚለቀቀው ውኃ ተጠልፎ እስከ 50ሺ ሄክታር የመስኖ እርሻ እንዲያጠጣ ታቅዶ ኤሌክትሪክ ማመንጨት ሥራ እንደጀመረ የ20ሺ ሄክታር ማሳ እንዲያለማ ተደርጎ ነበር።
በሌላ በኩል ከልማት ጋር ሣይያያዝ የተገነባው የፊንጫ ኤሌክትሪክ ማመንጫ ጣቢያ የሚለቀቀው ውኃ ያለጥቅም መፍሰሱን በመመልክት ለስኳር ፋብሪካ ጥሬ ዕቃ የሚሆን ሸንኮራ አገዳ በ10ሺ ሄክታር ማሳ እንዲያለማ ታቅዶ ሥራው ተጀምሮ ነበር።የጣናን ሃይቅ በማሳደግ የኤሌክትሪክ ኃይል ለማመንጨት ሲወሰን በተመሳሳይ መንገድ የሚለቀቀውን ውኃ በመጠቀም በበለስ ሸለቆ እስከ 100ሺ
ሄክታር የመስኖ እርሻ ለማት ለማካሄድ እንቅስቃሴው ተጀምሮ ነበር።በሌሎች አካባቢዎችም የኤሌክትሪክ ኃይል ለማመንጨት በሚታሰብበት ጊዜ የሚለቀቀው ውኃ ጥቅም ላይ ውሎ የአገራችንን ኤኮኖሚ ለማሳደግና በምግብም ራሳችንን እንድንችል እንዲረዳ ጎን ለጎን መታቀድ ነበረበት።
ከመስኖ ልማት ጋር ሳይያያዝ ግድብ መገንባትና ኤሌክትሪክ ማመንጨት የግብፅን ፍላጎት በፍቃደኝነት ማሟላት ማለት ነው።ግብፅ ሙሉ ወጪውን በመሸፈን በኢትዮጵያ ትላልቅ ግድቦችን ለመገንባት የኤሌክትሪክ ኃይል በማመንጨት የሚለቀቀውን ውኃ ሳይቀናነስ እንድትወስድ ማረጋገጫ ቢሰጣት ያለ ማቅማማት እንደምትስማማ በእርግጠኛነት መናገር ይቻላል።ግብፅ ውኃውን ከምንም ነገር አስበልጣ ስለምትፈልገው በኢትዮጵያ ግድቦች ቢገነቡና ኤሌክትሪክ በቻ እንዲመረት ቢደረግ ምንም ዓይነት ተቃውሞ አታሰማም።ለማስረጃ ያህል በጣና ሃይቅ የአባይ ወንዝ መውጪያ ላይ የተወሰነ ግድብ ተገንበቶ የጣና ውኃ መጠን እንዲጨምር ከተደረገ በኋላ በምዕራብ አቅጣጫ ጣና ተሸነቁሮ ውኃውን ቁልቁል በመልቀቅ ተርባይን እንዲያሽከረከር ተደርጎ የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጨት ከተጀመረ
ቆየት ብሏል፤ የተከዜ ወንዝ ተገድቦ የተጠራቀመው ውኃ እየተለቀቀ ኤሌክትሪክ ማምረት ከተጀመረ ዓመታት ተቆጥረዋል።ታዲያንስ ግብፅች የተጠራቀመ ውኃ በጣም በሚያስፈልጋቸው በድርቅ ጊዜ
ሳይቋረጥ የሚያገኙት መሆናቸውን ስለሚያውቁ ለምን በጣና ሃይቅ ኤሌክትሪክ ይመረታል፣በተከዜ ወንዝ ላይ ግድብ ተገንብቶ ኤሌክትሪክ ማመንጨት ለምን ተጀመረ ጥቅማችንን ይጎዳል ብለው አልተናገሩም ፤ ተቃውምም አላሰሙም፤ ምክንያቱ ተጠቃሚዎቹ እነሱ ናቸውና።
አባይን አስመልክቶ ይህን ያህል ከተነጋገርን ስለ’’ ታላቁ የሚሊኒዮም ግድብ’’ አንዳንድ ነገር ብናነሳ መልካም ይመስለኛል።እንደተነገረን ግድቡ የሚገነባው በቤኒሻንጉል ክልል ከሱዳን ድንበር 17 ኪሎሜትር ርቀት በሚገኝ ቦታ ላይ ነው። ግድቡ 62 ቢሊዮን ሜትር ኩብ ውኃ ይይዛል።የግንባታው ወጪ 80 ቢሊዮን ብር ሲሆን በኢትዮጵያ ሕዝብ መዋጮ ይሸፈናል ተብሏል።በግድቡ ውኃ ከ6ሺ በላይ ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል ይመነጫል።እንግዲህ ከግድቡ ኢትዮጵያ የምታገኘው ጥቅም የኤሌክትሪክ ኃይል ብቻ መሆኑ ነው።ግብፅና ሱዳን ግን ተጨማሪ ውኃ ያገኛሉ። ኤሌክትሪክ ኃይል ለማምረት ምን ያህል ተርባይኖች እንደሚተከሉ አይታወቅም።
6000ኪሎ ዋት ኤሌክትሪክ ለማምረት አንዱ ተርባይን 50 ሜጋ ዋት የሚያመነጭ ቢሆን እንኳን ከ 100 ተርባይኖች በላይ መተከል ይኖርባቸዋል።አንዱን ተርባይን ለማሽከርከር 5 ሜትር ኩብ ውኃ በሰኮንድ መልቀቅ ያስፈልጋል ቢባል እንኳን 100 ተርባይኖችን ለማሽከርከር 500 ሜትር ኩብ ውኃ በሰኮንድ መልቀቅ ያስፈልጋል ማለት ነው። አባይ ሲሞላ በክረምት ወራት ከተጠራቀመው ውኃ
ተርባይኖችን ለማሽከርከር መልቀቅ አስፈላጊ አይሆንም። ወንዙ በግድቡ ላይ ሰለሚያልፍ እግር መንገዱን ተርባይኖቹን እያሽከረከረ ያልፋል።በግድቡ የተከማቸውን ውኃ መልቀቅ የሚያስፈልገው በበጋ ወራት አባይ ሲደርቅ ነው።ተርባይኖች ከዓመት ዓመት መሽከርከር ሰለአለባቸው ከግድብ እየተለቀቀ የሚወርደው ውኃ በቋሚነት ያስፈልጋል። በዚህ አሠራር በክረምት ወራት አባይ ሲሞላ ከሚገኘው
የውኃ መጠን የበለጠ ግብፅና ሱዳን በበጋ ወራት ያገኛሉ ማለት ነው።ይህ መጠን በተፈጥሮ ከሚያገኙት በእጅጉ ይበልጣል።በተፈጥሮ የሚያገኙት ውኃ እየቆጨን እያለ እያንዳንዱ እትዮጵያዊ
እየተመጠጠ በተሰበሰበው ገንዘብ ትልቅ ግድብ ገድበን ውኃ አጠራቅመን በተጨማሪ መስጠታችን እንደሆነ የኢትዮጵያ ሕዝብ የተረዳው ወይም የተገነዘበው አይመስልም።ሕዝቡ የሚመስለው ወንዙ ተገድቦ ለልማት ውሎ ከረሃብ እንደሚወጣ ነው።
በጥቅሉ አባይ ሊገደብ ነው እየተባለ ይነገረዋል።በሚገደበው ግድብ ከሚከማቸው ውኃ አንድ ሄክታር መሬት እንኳን በመስኖ እንደማይለማ አይነገረውም። ከታላቁ ግድብ ጋር ምንም የመስኖ ልማት ፕሮግራም አልተያዘም። ወደፊት ውኃውን ለልማት እናውለዋለን እንዳይባል ከግድቡ በታች ለእርሻ የሚሆን መሬት የለም። በርባራ አካባቢ ነው፤ ከዚያም ቢሆን ውኃው ተለቆ ተርባይን ከአሽከረከረ በኋላ በቀጥታ ሱዳን ውስጥ ይገባል።ምክንያቱም በሱዳን ጠረፍና በግድቡ መሐል 17 ኪሎ ሜትር ብቻ እርቀት ነው ያለው።የውኃ ጉዳይ ለግብፅ የመኖር ወይም ያለመኖር ጥያቄ ነው። ከኢትዮጵያ
የምትወጣዋን ውኃ ትቆጣጠራለች። ይህ አዲሱ ግድብ ሥራው ተጠናቆ ኤሌክትሪክ ለማመንጨት ውኃ መልቀቅ ከጀመረ በኋላ ውኃውን ማቆም አይቻልም።ምክንያቱም ከዓመት ዓመት የሚፈሰው ውኃ እየተለካ ይመዘገባል።
ኤሌክትሪክ ማምረት አቆማለሁ ብላ ኢትዮጵያ ብታቆም ጦርነት እንደማወጅ ተቆጥሮ በግብፅና ከሱዳን ጋር ውጊያ መግጠምን ያስከትላል።በመሆኑም ዛሬ የሐገር ፍቅር ስሜታችንን ቀስቅሰው በሚገባ ግልፅ ሳይሆንልን የግድቡን ሥራ መደገፋችን ገንዘብ ማውጣታችን ወደፊት መዘዝ ያስከትልብናል። ‘አባይ ሊያለማን ወይስ ሊያጠፋን’ ብለን መጠየቅም ይኖርብናል። ግድቡ የመስኖ ልማት
ጋር ቢያያዝ ከረሃብ ከድህነት ልንወጣ ስለምንችል ማንኛውንም ዓይነት መስዋዕትነት ሕዝብ ቢከፍል ተገቢ በሆነ ነበር፤ ከሕዝብ ጎን ጋር ያልተዛመደ ግዙፍ ሥራ መወጠኑ በኋላ አሁን ለሚደረገው የሚያስጠይቅ ሊሆን ይችላል።
የሚገርመው ደግሞ ከዚህ ድንቅ ከተባለው ግድብ የሚገኘው የኤሌክትሪክ ኃይል ለሱዳንና ለግብፅ ይሸጣል መባሉ ነው።የሚሸጠውም በጣም በአነስተኛ ዋጋ ነው።በአሁኑ ጊዜ ለሱዳን አንድ ኪሎዋት የሚሸጠው በስድስት ሳንቲም የአሜሪካን ሲሆን፣ሱዳን በሃገሯ እስከአሁን የምትሸጠው ሃያ ስድስት ሳንቲም የአሜሪካ ነው።በዚህ ዓይነት የ ሃያ ሳንቲም ትርፍ ታገኛለች ማለት ነው። ሱዳንና ግብፅ በውኃችን የተነሣ ጠላት አድርገውን ብዙ ጎድተውናል።ወደፊትም ይጎዱናል። ሃገራችንን ለመከፋፈልና ለመገነጠል ለተሰለፉት ዛሬ ኤርትራን ገንጥለው ለሚያስዳድሩትና የኢትዮጵያን ሕዝብ በዘር በጎሣ ከፋፍለው ለሚመሩት ቡድኖች አጋር ሆነው ቆይተዋል።’አንዳንዴ የአባይ ግድብ ለነዚህ ሃገሮች ወሮታ ይሆን’ ብለው የሚጠይቁ ሃገር ወዳዶች አሉ። ታዲያ በዚህ የጠላትነት መንፈስ እየተመለከቱን እያሉ ኤሌክትሪክን ያህል የልማት ኃይል አቅራቢ ሆነን እንዲያድጉና እንዲበለጽጉ በወታደራዊ ቴክኒክና ቴክኖሎጂ እንዲዳብሩ መርዳታችን እንደሆነ መገንዘብ አልቻልንም።
ኤሌክትሪክ ለጎረቤት አገሮች የመሸጥ ሐሣብ በደርግ ዘመን ተነስቶ ነበር።የጦር መሣሪያ ከማስታጠቅ አይተናነስም ተብሎ ሐሣቡ ውድቅ ተደርጎ ነበር።ኢትዮጵያ የሚያስፈልጋትን የኤሌክትሪክ ኃይል ሌሎች ወንዞች ማመንጨት ይቻላል ተብሎ፤በግልገል ግቤ በርካታ ግድቦች ተገድበው በቂ የኤሌክትሪክ ኃይል የሚመረትበት ቦታ የሌለ ይመስል ታላቁ ግድብ ኤሌክትሪክ በኤሌክትሪክ ያደርገናል ችግራችን በሙሉ ይወገዳል፤እየተባለ የሚካሄደው አዳናጋሪ ፕሮፓጋንዳ ወደፊት ሃቁ መታወቁ አይቀርም።እኔ እንደምገምተው ከግብፅ ጋር ስምምነት አድርገው በጋራ የነደፉት ፕሮጀክት
ይመስለኛል።በጥናቱም ላይ የግብፅ እጅ ይኖርበታል የሚል ግምት አለኝ።የዚህ ግድብ ሥራ ግብፅን የሚጎዳ ቢሆን ኖሮ በዓለም ከፍተኛ ጩህትና የፖለቲካ ትረምስ ይሰማ ነበር። ግብፅ ያለችው ነገር ቢኖር ቴክኒካል ወረቀቶቹን ስጡኝ ነው፤ይህም ለማለት ያህል እንጂ ቴክኒካል ጥናቱ ቀድሞ በእጇ ይገኛል።
አሁን ለግብፅና ለሱዳን የሚጠቅም ሥራ ኢትዮጵያ በማንቀሳቀሷ ከዚህ በፊት በአባይ ጉዳይ ላይ አልነጋገርም፤ ስምምነትም በአዲስ መልክ አላደርግም ሲሉ የነበሩ ሁለቱ አገሮች በጉዳዩ ላይ ንደራደራለን የሚል አቋም ይዘዋል።የኢትዮጵያ ሕዝብ ገንዘብ ማውጣቱን እንዲቀጥል ብቻ አለፍ አለፍ እያሉ በለሆሳስ የግድቡ ሥራ አሳስቦናል ይላሉ። ዘለዓለማዊ የሃገር መታደግና ዕድገት ሳይሆን ዘለዓለማዊ ጠንቅ እንዳይተከልባት ለምን? ለማን? እንዴት? የሚለው የሃገር ጥቅም መለኪያ፣ሊተኮርበት ይገባል።ከራስ እያወለቁ ጠላትን እያስታጠቁ ግንባታ ስንኩል ስለሆነ አባይ መዘዝ ሳይሆን ሕዝብ አገዝ እንዲሆን ሁሉም ዕድሉ አሁን መሆኑን መገንዘብ ይገባዋል።

የመንግስቱ ኃይለማርያም አጃቢ “የሌ/ኮ መንግስቱ ያልተነገሩ ሚስጢሮች”የተሰኘ መጽሐፍ አሳትመው በተኑ

$
0
0

mengistu haile mariam(ዘ-ሐበሻ) ዙምባብዌ በስደት የሚገኙት የቀድሞው ፕሬዚዳንት መንግስቱ ኃይለማርያም በስማቸው የሚወጣው መጽሐፍ ቁጥር በ10ሮች የሚቆጠሩ ሲሆኑ እርሳቸው ግን አንድ መጽሐፍ ብቻ አውጥተዋል። “የመንግስቱ ትዝታዎች”። ዛሬ ደግሞ በአዲስ አበባና በመላው ኢትዮጵያ የፕሬዚዳንቱ የቀድሞ አጃቢ ያሳተመውና “የሌ/ኮ መንግስቱ ምስጢሮች” የተሰኘ መጽሐፍ መሰራጨቱን የዘ-ሐበሻ ዘጋቢዎች አስታውቀዋል።
በቀድሞ የኢትዮጵያ ፕሬዝዳንት መንግስቱ ሃይለማርያም የቤተመንግስትና የሥራ ህይወት ዙሪያ እንደተጻፈ የሚነገርለት ይኸው “የሌ/ኮ መንግስቱ ያልተነገሩ ሚስጥሮች” የተሰኘው መፅሀፍ የተጻፈው የቀድሞው ልዩ ኃይል አባል እና የፕሬዝዳንት መንግስቱ አጃቢ በነበሩት እሸቱ ወንድሙ ወልደስላሴ እንደሆነ ታውቋል። ይህ መጽሐፍ ባለ 120 ገፅ እንደሆነ የገለጹት የዘሐበሻ ዘጋቢዎች የመጽሐፉ ደራሲ ለ14 ዓመታት በልዩ ጥበቃነት መስራታቸውን አስታውቀዋል። እኚሁ የቀድሞው የመንግስቱ ኃይለማርያም አጃቢ ካሁን ቀደም “ህይወት በመንግስቱ ቤተመንግስት” በሚል ርዕስ ሁለት ቅፅ መጻሕፍትን ያሳተሙ መሆኑ ይታወሳል።

የፀረ ሽብርተኝነት ህጉ ለምን አያስፈራ? (በግርማ ሠይፈ ማሩ)

መሲ ባንቺም ኮራን –ከነብዩ ሲራክ

ቅዱስ ጊዮርጊስ በቱኒዚያው ክለብ 3 ለ 1 ተሸነፈ

$
0
0

St George
(ዘ-ሐበሻ) በአፍሪካ ኮንፌዴሬሽን ዋንጫ እየተካፈለ የሚገኘው የቅዱስ ጊዮርጊስ ክለብ በደጋፊው ፊት በቱኒዚያዊ ክለብ ሲ ኤስ ሰፋክሲን 3ለ1 ተሸነፈ። በውድድሩ በከቱኒዚያና ማሊ ክለቦች ጋር ተድልድሎ በመጫወት ላይ የሚገኘው ቅዱስ ጊዮርጊስ ዛሬ ኦገስት 18፣ 2013 በምድቡ መሪ ሲ ኤስ ሰፋክሲን 3ለ1 በመሸነፍ ደጋፊውን አንገቱን አስደፍቷል።

ሲ ኤስ ሰፋክሲን በምድቡ ያደረጋቸውን ሶስት ጨዋታዎች በማሸነፍ 9 ነጥብ እየመራ የሚገኝ ሲሆን ቅዱስ ጊዮርጊስ ስታዲ ማሊን አሸንፎና በኢቶልዲ ሳህልና ሲ ኤስ ሰፋክሲ ተሸንፎ በ3 ነጥብ ይዟል፡፡ በደጋፊው ፊት የቱኒዚያውን ሲ ኤስ ሰፋክሲን የገጠመው ጊዮርጊስ ጨዋታው ከባድ እንደሚሆንበት የስፖርት ተንታኞች ይናገራሉ።

የ ዶክቶር ገመቹ ከእውነታው የራቀ የተሳሳተ መረጃ

የድምጻዊ ኢዮብ መኮንን ቃለ ምልልስ ቪድዮ –ለትውስታ

$
0
0

ይህን ቃለ ምልልስ ያደረገው የቀድሞው የማህደር ጋዜጣ ዋና አዘጋጅና አሳታሚ ወርቅአፈራው አሰፋ ነው። ስለኢዮብ ግንዛቤ ሊሰጣችሁ ይችላልና ይመልከቱት።

“የሚያንጽ ካልሆነ በስተቀር ኔጊቲቭ የሆነ ዘፈን መዝፈን አልፈልግም”


ጋዜጠኛ ውብሸት ታዬና ዘሪሁን ገ/እግዚአብሔር ሊፈቱ ይሆን?

$
0
0

እስር ቤት የምትገኘው ጋዜጠኛ ሒሩት ክፍሌ

እስር ቤት የምትገኘው ጋዜጠኛ ሒሩት ክፍሌ

ዘጋቢ ጋዜጠኛ ስለሺ ሐጎስ

በእነ ኤልያስ ክፍሌ መዝገብ በሽብርተኝነት ክስ ተፈርዶባቸው በማረሚያ ቤት ከሚገኙት አራቱ ኢትዮጵያውያን መሀከል ጋዜጠኛ ውብሸት ታዬ፣ ወ/ሮ ሂሩት ክፍሌና አቶ ዘሪሁን ገ/እግዚአብሄር በ2004 ዓ.ም ይቅርታ የጠየቁ ሲሆን ምላሽ ሳያገኙ ለረዥም ጊዜ መቆየታቸው ሲያነጋግር ሰንብቷል፡፡ በተለይ ሲውዲናውያኑ ጋዜጠኞች ከኢትዮጵያውያኑ ጋር በተመሳሳይ ወቅት ይቅርታ ጠይቀው አፋጣኝ ምላሽ ማግኘታቸውና በአንጻሩ የእነውብሸት ይቅርታ ከአመት በላይ መዘግየቱ ተገቢ አለመሆኑ ሲገለጽ ቆይቷል፡፡

ከአንድ አመት በላይ ቆይታ በኋላ ሐምሌ 25 2005 ዓ.ም የይቅርታ ቦርድ ጽ/ቤት ማህተም አርፎበት ለወ/ሮ ሂሩት ክፍሌ በተላከ ደብዳቤ የይቅርታ ጥያቄያቸው ለፕሬዝዳንቱ ቀርቦ ውድቅ መደረጉ ተገልጾላቸዋል፡፡ ወ/ሮ ሂሩት ከእነ ውብሸት ጋር ባንድ መዝገብ ተከሰው 19 አመት የተፈረደባቸው ሲሆን የይቅርታ ጥያቄውንም ያቀረቡት በተመሳሳይ ወቅት ነው፡፡ ይሁን እንጂ ወደ ህትመት እስከገባንበት ጊዜ ድረስ ለጋዜጠኛ ውብሸት ታዬና ለአቶ ዘሪሁን ገ/እግዚአብሔር የደረሳቸው ደብዳቤ አለመኖሩን አረጋግጠናል፡፡

የወ/ሮ ሂሩት ይቅርታ በፕሬዝዳንቱ ውድቅ መደረጉን አስመልክቶ ልጃቸው ፍጹም መሰለ እናቱ ከተፈረደባቸው በኋላ ይግባኝ ከማለት ይልቅ ይቅርታ መጠየቅ የወሰኑበት ምክኒያት የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ መለስ ዜናዊ በፓርላማ ቀርበው “እንኳን ሀገር ውስጥ ያሉት ውጪ ያሉትም ቢሆኑ ዛሬ ይቅርታ ከጠየቁ ከነገ ጀምሮ ነጻ ናቸው” የሚል ቃል መግባታቸው እንደሆነ ገልጾ ይግባኝ የምንልበት አማራጭም አልፎ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከገቡት ቃል በተቃራኒ ይቅርታው ውድቅ ተደርጓል መባሉ እንዳሳዘነው ተናግሯል፡፡ ፍጹም አክሎም “ለሲውዲናውያን የተሰጠው ዕድል ለኢትዮጵያውያን ጨርሶ ይከለከላል የሚል ዕምነት ስለሌለን የይቅርታ ጥያቄውን በድጋሚ በሽማግሌዎች በኩል እናቀርባለን” ብሏል፡፡

የአቶ መለስ ዜናዊን ሙታመት አስመልክቶ በርካታ እስረኞችን ለመፍታት መንግስት በእንቅስቃሴ ላይ እንደሚገኝ ያረጋገጡት ምንጮቻችን ጋዜጠኛ ውብሸትና አቶ ዘሪሁን ደብዳቤ ያልደረሳቸው ከሚፈተቱት እስረኞች ዝርዝር ውስጥ ገብተው ሳይሆን እንደማይቀር ግምታቸውን አስቀምጠዋል፡፡

Health: ተፈጥሯዊ –ብጉር ማጥፊያዎች

$
0
0

ከሊሊ ሞገስ
እዚህ ሚኒሶታ አንዳንድ ሴቶች የሞንግ ወይም የቻይና ገበያ በመሄድ የፊት ሳሙናዎችን እና ቅባቶችን በመግዛት ቡግራችንን እናጠፋለን፤ መልካችንን እናቀላለን በሚል ካለ ሃኪም ትዕዛዝ ይህን ሳሙናና ቅባት በመጠቀም ፊታቸውን ሲያበላሹ አስተውለናል። አንዳንድ ሴቶችም ወደ ዘ-ሐበሻ በመደወል “ሳሙናውና ቅባቱ ፊታችንን አበላሸው፣ አዥጎረጎረን፣ ቡግር አወጣብን” ሲሉ በ እኛ የደረሰው እንዳይደርስ ምክራችንን አስተላልፉልን ብለውናል። የዘ-ሐበሻ የጤና አምድ ሁልጊዜም ሰዎች ሳሙናም ሆነ ፊት የሚያጠራ ቅባት ከመቀባት በፊት ከቆዳ ሃኪም ጋር መነጋገር እንደሚያስፈልግ ስትመክር ቆይታለች። የኤሲያኖች ቆዳ እና የሃበሾች ቆዳ አንድ አይነት አይደለም። እነርሱን ስለጠቀማቸው ሃበሾችን ይጠቅማል ማለት አይደለም። በመሆኑም የዚህ ችግር ስለባዎች ወደ ሃኪም እንዲሄዱ በመምከር ተፈጥሯዊ የቡግር ማጥፊያዎችን እንጠቁማለን። ይህንን ያዘጋጀነውም ለግንዛቤዎ እንዲጠቅም እንጂ ሁልጊዜም ቢሆን አንድ ነገር ከማድረግ በፊት ሃኪምዎን ማማከርዎን አይርሱ።
health
ቅባታማ ምርቶችን ያስወግዱ፡- ከፍተኛ የቅባትነት ይዘት ያላቸውን የፀጉር ቅባቶች ጨምሮ የፊት ማውዣዎች (moisturizers) እና ዘይታማ ማጽጃዎችን አይጠቀሙ፡፡
የፊትዎን ንፅህና ይጠብቁ፡- ፊትዎን የእጅዎ መዳፍ ላይ በፍፁም ማሳረፍ አሊያም በተደጋጋሚ ፊትዎን መዳሰስ አይኖርብዎትም፡፡ ፀጉርዎን አዘውትረው በሻምፖ ይታጠቡ፣ ነገር ግን ፊትዎን መንካት የለቦትም፡፡
የአካል እንቅስቃሴ ያዘውትሩ፡- በመካከለኛ ደረጃ የአካል እንቅስቃሴ ማዘውተርዎ የደም ዝውውርን ከማቀለጣጠፉም በላይ መርዛማ ንጥረ ነገሮች ከሰውነትዎ እንዲወገዱ ለማድረግ ይረዳል፡፡
ከጭንቀት ነፃ ይሁኑ፡- በርካታ ጥናቶች ጭንቀት ብጉርን ከማባባሱም በላይ የቆዳ ጤንነት ችግር ላይ እንዲወድቅ ያደርጋል ይላሉ፡፡ ጭንቀት ሲያድርብዎ ከወዳጆችዎ ጋር ይማከሩ፣ የሚወዱትን ሙዚቃ ያዳምጡ፣ አሊያም ዘና ለማለት ይሞክሩ፡፡ የእግር ጉዞ ማድረግዎ ዘና እንዲሉ ያደርጋል፡፡ እነዚህን ጨምሮ ሌሎች ከጭንቀት ነፃ እንዲሆኑ የሚረዱም ነገሮችንም ይከውኑ፡፡
በቂ የፀሐይ ብርሃንና ኦክስጅን፡- የሐይ ብርሃን ቫይታሚን ዲን ለሰውነታችን ይሰጣል፡፡ ይህ ቫይታሚን ለቆዳ ጤንነት በጣም አስፈላጊ ነው፡፡ ንፁህ አየርና የፀሐይ ሙቀት ጭንቀትን በመቀነስ በቆዳ ውስጥ የኦክስጅን መጠን እንዲጨምር ያደርጋሉ፡፡ ይሁን እንጂ ፀሐይ ላይ ለረጅም ጊዜ በመቆየት ቆዳዎ እንዲቆጣ ማድረግ አይኖርብዎትም፡፡
ብጉርን ለመቀነስና ለማጥፋት ይረዳሉ ተብለው የሚመረቱ ዘመናዊ ባህላዊ ቅባቶችና ዘይቶች በርካታ ናቸው፡፡ ብዙዎቹ ለጊዜው ችግሩን ያጠፉ ቢመስሉም ቅባቱ ካለቀ በኋላ ግን ብጉሩ ተባብሶ ሊቀጥል የሚችልበት ዕድል ሰፊ ነው፡፡ ከባህላዊም ሆነ ዘመናዊ ህክምናዎች ባልተናነሰ ተፈጥሯዊ የሚባሉት ዘዴዎች ከፍተኛ የሆነ ጠቀሜታ ይሰጣሉ፡፡ ጥቂቶቹ የሚከተሉት ናቸው፡፡
ብጉሮችን በጣትዎ አይነካኩ፡- ፊትዎ ላይ የሚታዩትን ብጉሮች በጣትዎችዎ መጫን ወይም ማሸት አይገባም፡፡ እንዲህ በሚያደርጉበት ጊዜ የፈሳሹን (sebum ይሰኛል) መጠን እንዲጨምር ከማድረግዎም በላይ ከቆዳዎ ስር ያለው አካል (membrane) እንዲቀደድ ያደርጋሉ፡፡ ኢንፌክሽኑና ፈሳሹ በቆዳዎ ስር በመዛመት ሌሎች ብጉሮች እንዲፈጠሩም ምክንያት ይሆናል፡፡ ከሁሉም በላይ በፊትዎ ላይ የማይጠፉ ጠባሳዎች የመከሰት ዕድልን እንዲጨምር ሊያደርጉ ስለሚችሉ ፊትዎን በጣትዎችዎ ማሸትን ያስወግዱ፡፡
ፊትዎን በቀን ሁለት ጊዜ በሳሙና ይታጠቡ፡- ፊታቸው ላይ ብጉር የሚታይባቸው ሰዎች ከሰልፈር (sulfur) የተሰሩ ሳሙናዎችን እንዲጠቀሙ ይመከራል፡፡ ቆዳዎ በተፈጥሮው ባለ ወዝ (oily) ከሆነ benzoyl peroxide የተካተተበት ሳሙና ይጠቀሙ፡፡ ፊትዎን በስፖንጅና በሌሎችም ሻካራ ጨርቆችና ብሩሾች እየሞዠቁ እንዳያጥቡ፡፡
- ብጉሩን ያብሰዋል እንጂ አያጠፋውም፡፡
ፊትዎን ከሁለት ጊዜ በላይ ደጋግመው በማጠብ እንዳያደርቁት መጠንቀቅ ይኖርብዎታል፡፡ የቆዳ ዕጢዎች ፊትዎ የደረቀ ከመሰላቸው ብዙ sebum እንዲመረት በማድረግ ብጉሩ እንዲስፋፋ ምክንያት ይሆናሉ፡፡
ምግብና ብጉር፡- ለበርካታ ሰዎች የምግብ አለርጂ ለረጅም ጊዜ የማይጠፋ ብጉር እንዲፈጠርባቸው ሊያደርግ ይችላል፡፡ ብጉር ፊታቸው ላይ የሚታይባቸው ሰዎች ቅባትና ቅመማ ቅመም የበዛባቸው ምግቦች አብዝተው እንዲወስዱ ይመከራል፡፡ የቅርብ ጊዜ ጥናቶች በወተት ውስጥ የሚገኙ ሆርሞኖችና በባህር ምግቦች ውስጥ የሚገኘው ከፍተኛ የአዮዲን መጠን ብጉርን እንደሚያባብሱ ተደርሶበታል ይላሉ፡፡ ከተቻለ እነዚህ ምግቦች አይወሰዱ፡፡ ከእነዚህ በተጨማሪ ስኳር፣ የወተት ተዋፅኦዎች፣ ለረጅም ሰዓት ሲጠበሱ የቆዩ ምግቦች፣ ስጋ፣ የኦቾሎኒ ቅቤ እና የመሳሰሉት ቅባታማና ዘይታማ ምግቦችን ያስወግዱ፡፡ ከዚህ በተቃራኒው አረንጓዴ ተክሎች፣ የአትክልት ጭማቂና በዚንክ የበለፀጉ ምግቦች ብጉርን ለመቀነስ ይረዳሉ፡፡
ውሃ ይጠጡ፡- ሲባል በመጠኑ በርከት ያለ መሆን ይኖርበታል፡፡ ጄኒፈር ቶደን የተባሉ የብጉር ኤክስፐርት በቀን ስምንት ብርጭቆ ውሃ በመጠጣት ብጉርን መከላከል እንደሚቻል ይመክራሉ፡፡ ምክንያቱ ደግሞ ውሃ ቆሻሻን ከሰውነታችን ሲስተም ማስወገድ ስለሚችል ነው፡፡ ይህ ደግሞ ሰውነታችን ብጉርን እንዲከላከልና እንዲያድን ይረዳዋል፡፡
ሜክአፖችን አይጠቀሙ፡- የተለያዩ የሜክአፕ ምርቶች ብጉርን ሊያስከትሉ ስለሚችሉ በተቻለ መጠን ባይጠቀሟቸው ይመከራል፡፡ እነዚህ መኳኳያዎች ብጉር እንዲስፋፋ ያደርጋሉ፡፡ የግድ መጠቀም አለብኝ ካሉ ደግሞ መሰረታቸው ውሃ የሆነ (water based) ሜክአፖችን ምርጫዎ ያድርጉ፡፡ የሜክአፕ ብሩሾችዎን በቋሚነት ያጽዱ፤ እንዲሁም ወደ መኝታዎ ከመሄድዎ በፊት ፊትዎንና ሜክአፕ የነካውን አካል ይታጠቡ፡፡
የወይራ ዘይት
- የጓሮ አትክልት መንከባከቢያ ቁሳቁሶችን በቀላሉ ለማጽዳት ያስችላል፡፡
- የቤትና የቢሮ ፈርኒቸር ያሳምራል፡፡
- በቀላሉ ከዓይን ላይ ሜክአፕ ለማስለቀቅ ይረዳል፡፡
- ከማይዝግ ብረት የተሰሩ (stainless steel) ቁሶች እንዲያንፀባርቁ ያደርጋል፡፡
- የካጄት አሊያም የሱሪዎ ዚፕ ተቀርቅሮ አልንቀሳቀስ ካለ የወይራ ዘይት ጠብ ያድርጉበት፡፡
- የቆዳዎን ልስላሴ ይጠብቃል፡፡
- ማንኳራፋትን ያስወግዳል፡፡
- የኩራዝ መብራት ሆኖ ማገልግል ይችላል፡፡
- አንዳንድ ስቲከሮች የተዉትን ማጣበቂያ ያስወግዳል፡፡
- ለጉሮሮ ህመም ፈውስ ይሰጣል፡፡
- የጆሮ ህመምን ያስታግሳል፡፡
- ጺምዎን ከተላጩት በኋላ ጥቂት የወይራ ዘይት ይቀቡት፡፡ ልስላሴው ያስደስትዎታል፡፡
- ጫማዎን ቢጠርጉበት ያሳምርልዎታል፡፡
- ጥሩ የፀጉር ቶኒክ ነው፡፡
- ገላዎን ገንዳ ውስጥ የሚለቃለቁ ከሆነ የወይራ ዘይት ጠብ ያድርጉበት፡፡ S

ድምጻዊ ኢዮብ መኮንን አረፈ

$
0
0

eyob
(ዘ-ሐበሻ) ትናንት ለሕክምና ወደ ናይሮቢ አምርቶ የነበረው ድምፃዊ ኢዮብ መኮንን ማረፉ ተዘገበ። ድምፃዊው ዘወትር እንደሚያደርገው ሁሉ በብስክሌት ሰውነቱን አፍታቶ ወደቤቱ ሲመለስ (የእህቱን ልጅ ት/ቤት አድርሶ ከተመለሰ በኋላ የቤቱን መጥሪያ እንደተጫነ መውደቁ) ወደ ሆስፒታል ለመሄድ ምክንያት እንደሆነውና በቅዱስ ገብርኤል ሆስፒታልም በተደረገለት ህክምና ሊነቃ ያልቻለው ድምፃዊው በኢትዮጵያውያን መዋጮ ወደ ናይሮቢ ለህክምና ትናንት ከተጓዘ በኋላ በጤናው ላይ መሻሻል ታይቶበት እንደነበር ዘገባዎች ጠቁመው ዛሬ ሕይወቱ ልታልፍ መብቃቷን ገልጸዋል።

በጅጅጋ ከተማ ተወልዶ ያደገውና “አንድ ቃል” በተሰኘው የመጀመሪያ አልበሙ ተወዳጅነትንና እውቅናን ያተረፈው ድምፃዊ ኢዮብ መኮንን ለሞት ያበቃው “ስትሮክ” ተብሎ የሚታወቀው በሽታ እንደሆነ ዘገባዎች ጠቁመዋል። ባለቤቱ ወ/ርፕ ወ/ሮ ቲና ተአረ ትናንት በአዲስ አበባ ታትሞ ለወጣው አዲስ አድማስ ጋዜጣ ጤንነቱ እየተሻሻለ መምጣቱን ገልጻ የነበረ ቢሆንም ለተጨማሪ ህክምና ወደ ኬንያ አምርቶ ሕይወቱ አልፋለች።

ዘ-ሐበሻ ለአርቲስቱ አድናቂዎች እና ቤተሰቦች መጽናናትን ትመኛለች። በ38 ዓመቱ ያረፈውን አርቲስትም አምላክ ሕይወቱን በገነት እንዲያቆያት እንመኛለን።

ኢዮብን ለሞት ስላበቃው ስትሮክ በሽታ ማወቅ ከፈለጉ ይህን ይጫኑ

Health: አርቲስት ኢዮብ መኮንን ለሞት ያበቃው ስትሮክ (Stroke) በሽታ ምንድን ነው?

$
0
0

- በዓመት ለ5 ሚሊዮን ሰዎች ሞት መንስኤ ነው
– ለድንገተኛ ሞት እና አካል ጉዳት ይዳርጋል
– ማንን ያጠቃል? ወንዶችን ወይንስ ሴቶችን?
– መነሻው እና መፍትሄውስ ምንድን ነው?

የግንባታ ተቆጣጣሪ መሀንዲስ የሆኑት አቶ ግዛቸው ጉደታ ከ25 ዓመት በላይ አገራቸውን በግንባታው ዘርፍ አገልግለዋል፡፡ የዛሬን አያድርገው እና የእሳቸው ሞያዊ አሻራ ያረፈባቸው ትልልቅ ሆቴሎች፣ ትምህርት ቤቶች፣ ህክምና ተቋማት እና የመንግስት ድርጅቶች በርካታ እንደሆኑ በኩራት ይናገራሉ፡፡ ዛሬ ግን አቶ ግዛቸው እንደበፊቱ የውብ ህንፃዎችን ዲዛይን ተቆጣጥሮም የማሰራት አቅማቸውን አጥተዋል፡፡ ምክንያቱም አቶ ግዛቸው ከየካቲት 8/2002 ዓ.ም ካጋጠማቸው ድንገተኛ አደጋ በኋላ መንቀሳቀስ ተስኗቸዋል፡፡
አንደበታቸውም አልፈታ ብሎ የሚናገሩት በግድ ነው፡፡ በዕለቱ የገጠማቸው አደጋም ህይወታቸውን ሙሉ ለሙሉ ቀይሮታል፡፡ በዚህም የተነሳ አቶ ግዛቸውም ሆኑ ቤተሰቦቻቸው ይህቺን ቀን ሁሌም ያስታውሷታል፡፡ በየዓመቱም አስበዋት ይውላሉ፡፡
በጠንካራና ታታሪ ሰራተኝነታቸው ይታወቁ የነበሩት አቶ ግዛቸው ሁሌም እንደሚያደርጉት በዚያች ‹‹የተረገመች›› በሚሏት ቀን በጠዋት ነበር በስራ ቦታቸው ላይ የተገኙት፡፡ አልፎ አልፎ ከሚያስቸግሯቸው የደም ግፊት ህመም በስተቀር ሙሉ ጤነኛ የነበሩት አቶ ግዛቸው በዕለቱ ግን ከጠዋት ጀምሮ አንዳች የመጫጫን ስሜት ይሰማቸው እንደነበር ያስታውሳሉ፡፡ ‹‹ትኩረት አልሰጠሁትም እንጂ ከሳምንታት ጀምሮም ሰውነቴ ድክም ይልብኝ ነበር፡፡ ብርድ ብርድም የማለት ስሜትም ያስቸግረኝ ነበር›› ይላሉ፡፡ አቶ ግዛቸው በዕለቱ ሰዓታትን ከፈጀው እና በጭቅጭቅ የተሞላ ከነበረው የድርጅት ስብሰባ በኋላ ድንገት የበረታ ህመም ይሰማቸው ጀመር፡፡
‹‹ህመሙ ሲበረታብኝ 8 ሰዓት አካባቢ ፍቃድ ጠይቄ ወደ ቤት ሄጄ ለማረፍ ወስኜ መንገድ እንደጀመርኩ ነገሮች ተለዋወጡ›› የሚሉት አቶ ግዛቸው ወደ መኖሪያ ቤታቸው በማምራት ላይ ሳሉ በድንገት መንገድ ላይ ራሳቸውን ስተው ወደቁ፡፡ በአካባቢው በነበሩ ሰዎች እርዳታ በቅድሚያ ሆስፒታል እንዲገቡ ተደረገ፡፡ ከዚያች ቀን በኋላ ራሳቸውን ለአንድ ወር ስተው የቆዩ ሲሆን ሲነቁ በህክምና ባለሞያዎች እና ቤተሰቦቻቸው በፊት ሰምተውት የማያወቁትን ችግር ስም ጠሩላቸው፡፡
eypb
‹‹ስትሮክ አጋጥሞህ ነበር›› ብለው ለአንድ ወር ራሳቸውን እንዲስቱ ያደረጋቸው ስትሮክ የሚባለው ድንገተኛ ችግር እንደሆነ ገለፁላቸው፡፡ ችግሩ ጥሎባቸው ያለፈው ጠባሳ ወደ ተለያዩ ውስብስብ ችግሮች ሊያመራቸው እንደሚችል የሰጉት ሐኪሞችም ለተጨማሪ ህክምና ወደ ውጪ አገር እንዲሄዱ የሚረዳ ማስረጃ ሰጧቸው፡፡ አቶ ግዛቸው ለህክምና ወደ ህንድ በማምራት በርካታ ገንዘብ ከስክሰው ብዙ ህክምና ማግኘት ቢችሉም እጅ እና እግሮቻቸው ዳግም መስራት እንደማይችሉ ሲነገራቸው በእሳቸውም ሆነ በቤተሰባቸው ላይ የደረሰው ድንጋጤ እና ሀዘን ከፍተኛ ነበር፡፡
አንደበታቸው እንደፈለጉት አልፈታ ብሎ እና ሁለት እግራቸውና እጃቸው አልታዘዝ ብሎ ቤት መዋል ከጀመሩ ሁለት ዓመት ያለፋቸው አቶ ግዛቸው ‹‹ስትሮክ በድንገት መጥቶ በግማሽ ገድሎኝ ሄዷል፡፡ መስራት እየቻልኩ የልጆቼ ጥገኛ አድርጎኛል፡፡ ሀብት እና ንብረቴንም አሳጥቶኛል፡፡ የሰው ሸከምም አድርጎኛል›› በማለትም ያማርራሉ፡፡ ‹‹ቀደም ባሉት ዓመታት ስለስትሮክ ሰምቼ አላውቅም ነበር፡፡ ሞኝ በራሱ ይማራል እንደሚባለው እኔም ሲደርስብኝ አወኩት›› ይላሉ አቶ ግዛቸው፡፡
አቶ ግዛቸውም ሆኑ ቤተሰቦቸው በድንገት ስለተከሰተባቸው የስትሮክ ችግር ያላቸው ግንዛቤ እጅግ አነስተኛ ነው፡፡ የዓለም ጤና ድርጅት ያደረጋቸው ጥናቶችም ስትሮክ በብዙዎች የማይታወቅ ነገር ግን ብዙዎችን እየጎዳ ያለ ችግር መሆኑን ይጠቁማል፡፡ ድርጅቱ ስትሮክ እያደረሰ ካለው የአካል ጉዳት እና ድንገተኛ የሞት አደጋ በመነሳት ለስትሮክ ህመም ‹‹ድንገተኛ መቅሰፍት›› የሚል መጠሪያ ሰጥቶታል፡፡ በአገራችንም ስትሮክ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ እንደ አቶ ግዛቸው የብዙዎችን በር እያንኳኳ ነው፡፡ ነገር ግን ብዙዎች ስለስትሮክ ያላቸው ግንዛቤ አነስተኛ ነው፡፡

የስትሮክ ሀ…ሁ
ስትሮክ ወይንም ‹‹ሴሬብራል ቫስኩላር አክሲደንት›› አንጎል እና የደም ስር ላይ ከሚደርሱ ህመሞች አንዱ ነው፡፡ ባለሞያዎች ስትሮክ ድንገተኛ የሆነ አንጎል ውስጥ የደም ስርጭት መዛባት ችግር እንደሆነ ይገልጻሉ፡፡ ስትሮክ በአንጎላችን ውስጥ የደም ስርጭት መቀነስን ወይንም መጨመርን ተከትሎ የሚከሰት ህመም መሆኑ ይነገራል፡፡ በዓለም ደረጃ በከፍተኛ ፍጥነት እየጨመረ እንደመጣ የሚነገርለት ስትሮክ በዓመት በርካታ ሰዎችን ለድንገተኛ ሞት እንዲሁም አካል ጉዳት እየዳረገ ይገኛል፡፡
በዓለም ላይ ያለው የስትሮክ ህመም ስርጭት በትክክል አይታወቅም፡፡ ነገር ግን የዓለም ጤና ድርጅት በአንጎል እና በደም ስሮች ላይ በሚከሰቱ ህመሞች ዙሪያ ያደረጋቸው ጥናቶች እንደሚጠቁሙት ስትሮክ በተለይ በአደጉ አገሮች ከልብ ህመም እና ከካንሰር በመቀጠል ሶስተኛ የሞት መንስኤ እንደሆነ ይጠቁማል፡፡
በአሜሪካን አገር ለምሳሌ ስትሮክን ጨምሮ በአንጎል እና በደም ስር ላይ የሚደርሱ ህመሞች በዓመት ከ200,000 በላይ ሰዎችን ለሞት ይዳርጋሉ፡፡ በእንግሊዝም ስትሮክ ተመሳሳይ ስፋት ያለው ጉዳትን ያደርሳል፡፡ ጥናቶች እንደሚጠቁሙት በተለይ በአሜሪካ እና በአውሮፓ ብቻ በስፋት ይታይ የነበረው ስትሮክ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በማደግ ላይ በሚገኙ አገሮችም በስፋት መታየት ጀምሯል፡፡ በተለይ አፍሪካ እና ደቡብ አሜሪካ ላይ ስትሮክ ብዙ ጉዳት እያደረሰ ነው፡፡ በዓለም አቀፍ ደረጃም በስትሮክ እና ተያያዥ ህመሞች በዓመት እስከ 5 ሚሊዮን የሚደርሱ ሰዎች ለህልፈተ ህይወት ይዳረጋሉ ተብሎ ይታመናል፡፡
እንደ የዓለም ጤና ድርጅት ጥናት በመጪዎቹ ዓመታት በዓለም ላይ ከሚከሰተው የስትሮክ ችግር ከፍተኛውን ቁጥር (75 ከመቶ) የሚይዙት የታዳጊ አገራት ዜጎች እንደሆኑ ይገልፃል፡፡ አሁንም ቁጥሮች እንደሚጠቁሙት በዓለም ላይ ከሚከሰተው ከስትሮክ ህመም ጋር የተያያዘ ሞት አብዛኛው ስለበሽታ ባለማወቅ እና ህክምናውን በቶሎ ባለማግኘት እንደሆነ ይነገራል፡፡
ከላይ ለመግለፅ እንደተሞከረው ስትሮክ በአንጎል ውስጥ የሚከሰት ድንገተኛ የደም ስርጭት መዛባት ችግር ሲሆን በዋናነትም የሚጎዳው የአንጎል ሴሎችን ነው፡፡ እንደ ባለሞያዎች እምነት አንጎል ላይ የሚደርስ ጉዳት ደግሞ ጉዳቱ እንደደረሰበት የአንጎል ክፍል፣ እንደ ጉዳቱ መጠን እና የስርጭት ስፋት ሌሎች የነርቭ ስርዓቶችን በመጉዳት ለተለያዩ ችግሮች ያጋልጣል፡፡
የአሜሪካን የህክምና ባለሞያዎች ማህበር ዓመታዊ ጆርናል የስትሮክ ህመም ሶስት ዋና ዋና ደረጃዎች እንዳሉት ይገልፃል፡፡ በዚህም መሰረት ድንገተኛው ስትሮክ በዋናነት የሚጎዳው አንጎላችንን ነው፡፡ አንጎል ላይ የሚደርስ ጉዳት ደግሞ በመቀጠል የደም ስሮቻችን እና የነርቭ ስርዓትን ይጎዳል፡፡ እነዚህ ጉዳቶች ደግሞ በአብዛኛው ሰዎች ለድንገተኛ ሞት እንዲጋለጡ የሚያደርግ ሲሆን አልፎ አልፎ ደግሞ እንደ አቶ ግዛቸው ሰዎችን ለከፍተኛ አካል ጉዳት በመዳረግ የሰዎችን እና የሰዎች የህይወት አቅጣጫ በማስቀየር ለበርካታ ግለሰባዊ፣ ቤተሰባዊ እና ማህበራዊ ችግሮች ይዳርጋል፡፡
የስትሮክ መምጪያ መንገዶች
አቶ ግዛቸውን ጨምሮ ብዙ ሰዎች ስለስትሮክ ህመም መንሰኤም ሆነ ለህመሙ ሊያጋልጡ ስለሚችሉ ነገሮች ያላቸው ግንዛቤ አነስተኛ ነው፡፡ በስትሮክ ህመም ህክምና ላይ ስፔሻላይዝ ያደረጉት ዶ/ር አንቶኒዮ ጉቲሬዝ የስትሮክ ህመም መንስኤ ምን እንደሆነ በትክክል እንደማይታወቅ ይገልፃሉ፡፡ ነገር ግን ዋና ዋና አጋላጭ ምክንያቶችን በሚል የሚከተሉትን ነገሮች በመንስኤነት ያቀርባሉ፡፡
እንደ ዶ/ር አንቶኒዮ ገለፃ በአንጎል ውስጥ በሚከሰት ድንገተኛ የደም ስርጭት መዛባት የሚገለፀው ስትሮክ የሚከሰተው የደም ስሮች መጥበብን፣ በተለያዩ ምክንያቶች የደምስሮች በድንገት መቀደድን እና ደም በዘፈቀደ አንጎል ውስጥ መፍሰስን፣ በተለያዩ ምክንያት በሚከሰት የደም መርጋት ችግር የተነሳ ወደ አንጎል የሚደረገው የደም ስርጨቱን ማስተጓጎልን፣ የደም ስሮች በድንገት መኮማተርን ተከትሎ እንደሆነ ይጠቁማሉ፡፡
ከዚህ በተጨማሪ በተለያዩ ህመሞች የተነሳ የደም ዝውውር መስተጓጎል፣ በተለይ ደግሞ በደም ግፊት እና በስኳር ህመም መጠቃትን ተከትሎ አንጎል ውስጥ ያለው የደም ፍሰት ስርዓት መዛባት፣ በተለያዩ የደም ስር ህመሞች መጠቃት እንደ ዶ/ር አንቶኒዮ ገለፃ የስትሮክ ዋነኛ መምጫ መንገድ ነው፡፡ እንደ የዓለም ጤና ድርጅት እምነት የደም ግፊት ህመም፣ የልብ በሽታ፣ አዘውትሮ የአካል ብቃት እንቅስቃሴ አለማድረግ፣ የተለያዩ የነርቭ በሽታዎች፣ አዘውትሮ ሲጋራ ማጨስ፣ የአልኮል መጠጦችን ማዘውተር፣ የስኳር ህመም፣ የዕድሜ መግፋት፣ የሰውነት ክብደት መጨመር እና የሰውነት ስብ ክምችት መብዛት፣ በተለይ ሴቶች ላይ ደግሞ የተለያዩ የወሊድ መከላከያ እንክብሎች በብዛት መጠቀም እና በደማችን ውስጥ የቀይ ደም ሴሎች ከመጠን በላይ መብዛት ለስትሮክ ዋና ዋና አጋላጭ ምክንያቶች እንደሆኑ ይጠቁማል፡፡
‹‹ከሁሉም በላይ ግን የደም ግፊት እና በቁጥጥር ስር መዋል ያልቻለ ስኳር ህመም ለስትሮክ ዋነኛ አጋላጭ ምክንያቶች ናቸው፡፡ በተለየ መልኩ ደግሞ የአመጋገብ ባህላችን፣ የአካል እንቅስቃሴ አለማድረግ፣ ረጅም ሰዓት ተቀምጦ መዋል የስትሮክ ዋነኛ መንስኤ ነው›› ይላሉ የስትሮክ ህመም ስፔሻሊስት የሆኑት ዶ/ር አንቶኒዮ፡፡
እንደ ዶ/ር አንቶኒዮ ገለፃ ቀደም ባሉት ዓመታት ስትሮክ ዕድሜያቸው በገፋ ሰዎች ላይ ብቻ ይከሰት የነበረ ቢሆንም ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ግን ወጣቶችንም ሆነ ጎልማሶችን በስፋት እያጠቃ መሆኑ ችግሩን ይበልጥ አሳሳቢ ያደርገዋል፡፡ ስትሮክ ከሴቶች ይልቅም በብዛት በወንዶች ላይ የሚከሰት ሲሆን ከላይ በመንስኤነት ከተጠቀሱ ነገሮች በተጨማሪ ስትሮክ በዘር የመተላለፍ ዕድሉም ከፍተኛ እንደሆነ ዶ/ር አንቶኒዮ ይናገራሉ፡፡
stroke
ማወቅ ደጉ
በህክምና ባለሞያዎች በተደጋጋሚ የሚነገር አንድ አባባል አለ፡፡ ‹‹ታሞ ከመማቀቅ አስቀድሞ መጠንቀቅ›› የሚል አባባል፡፡ ታዲያ ማንኛውንም በሽታ ሳይከሰት በፊት መከላከል የሚበረታታ ሲሆን ከተከሰተ በኋላም በቶሎ ህክምና ማግኘት የበሽታውን ስፋት ይቀንሳል፡፡ በቶሎ ህክምና ማግኘት የሚቻለው ደግሞ የህመሙን ምልክቶች ማወቅ ሲቻል ነው፡፡
ታዲያ እንደ አቶ ግዛቸው ብዙ ሰዎች ስለስትሮክ ያላቸው ግንዛቤ አነስተኛ ስለሆነ ችግሩ ከደረሰባቸው በኋላ እንጂ ቀደም ብሎ ስለሚያሳየው ምልክቶች ብዙም አያውቁም፡፡ በዚህም የተነሳ በቀላሉ መታከም በሚችሉ ህመሞች ለከፍተኛ ችግር ሲዳረጉ እንመለከታለን፡፡ ብዙ የህክምና ባለሞያዎች ስትሮክ ግልፅ የሆነ የህመም ምልክት እንደሌለው ቢናገሩም ዶ/ር አንቶኒዮ ግን የስትሮክ ህክምና ምልክቶችን የህመሙን አይነት፣ መንስኤ እና ጉዳት የደረሰበት የአንጎል ክፍል መሰረት በማድረግ የተለያዩ የህመሙን ምልክቶች ይዘረዝራሉ፡፡
እንደ ዶ/ር አንቶኒዮ ገለፃ ስትሮክ በሶስት ይከፈላል፡፡ አንጎል ውስጥ የሚገኙ ደምስሮች ግድግዳ መጥበብን ተከትሎ የሚከሰተው ስትሮክ የመጀመሪያው ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ የአንጎል ደምስሮች በመበሳት የተነሳ የሚከሰት ነው፡፡ ወደ አንጎል የሚደርሰው ደም እጥረት ደግሞ ሶስተኛ ነው፡፡
እንደ ዶ/ር አንቶኒዮ ገለፃ በተለይ የደም ግፊት እና የስኳር ህመም ባለባቸው ሰዎች ላይ በድንገት የሚከሰት የራስ ምታት ህመም፣ በተደጋጋሚ ማስመለስ፣ የማቅለሽለሽ ስሜትን ማስተናገድ፣ የማጅራት አካባቢ ህመም እና የማጅራት መገታተር፣ ድንገተኛ ፊት መጣመም እንዲሁም እጅ እና እግር መዛል እና የጡንቻዎች መዛል፣ በድንገት ግማሽ ወይንም ሙሉ የአካል ክፍል መደንዘዝ፣ የእጅ፣ የእግር እና የፊት ህመም የህመሙ ዋነኛ ምልክቶች ናቸው፡፡
በተለይ ስትሮክ ከመከሰቱ በፊት ባሉት ሳምንታት በድንገት ብርድ ብርድ ማለት፣ የጡንቻዎች ህመሞች፣ የሰውነት በቀላሉ መድከም፣ የመናገር ችግር እና የአንደበት መያያዝ ችግር መከሰት፣ መንተባተብ፣ ጆሮ ላይ የሚደርስ ጉዳትን ተከትሎ የሰዎችን ንግግር ለመስማት እና ለመረዳት መቸገር፣ አካላዊ ሚዛን ለመጠበቅ መቸገር፣ ሲንቀሳቀሱ መንገዳገድ፣ የእጅ እና የእግር ጡንቻዎች መንቀጥቀጥ፣ የእይታ አቅም መቀነስ (የእይታ የጥራት መቀነስ እና ብዥታ) እንዲሁም ሽንት እና ሰገራን መቆጣጠር አለመቻል የስትሮክ ህመም ዋነኛ ምልክቶች ናቸው፡፡
አቶ ግዛቸው ደግሞ ከራሳቸው ተሞክሮ በመነሳት ከእነዚህ ህመሞች በተጨማሪ ችግሩ ከመከሰቱ በፊት በተደጋጋሚ ራስን መሳት፣ እንቅልፍ ማጣት ወይንም እንቅልፍ እንቅልፍ ማለት በተለይ ሌሊት ላይ ደግሞ መቃዠት እንዲሁም የድብርት ስሜት በተደጋጋሚ ይሰማቸው እንደነበረ ይናገራሉ፡፡
ስትሮክ እና አንጎል
እንደሚታወቀው የሰውነታችንን አሰራር በዋናነት የሚቆጣጠረው አንጎላችን ነው፡፡ አንጎላችን ደግሞ ስራውን ለመስራት አስፈላጊ የሆኑ ግብአቶችን የሚያገኘው በደም አማካኝነት ነው፡፡ በማንኛውም ሰዓት የደም አቅርቦት ችግር ሲከሰት አንጎል ተግባሩን በአግባቡ ለመወጣት ይቸገራል፡፡ ስለዚህ ወደ አንጎል የሚደረገው የደም ስርጭት በማንኛውም ሰዓት የተስተካከለ መሆን አለበት፡፡
አንጎላችን ድንገተኛ የደም ስርጭት ችግር ሲገጥመው በቅድሚያ የተለያዩ አማራጮችን በመፈለግ ችግሩን ለመፍታት ጥረት ያደርጋል፡፡ በሌሎች የደም ስሮች አማካኝነት ወይንም በመጥበብ እና በመበሳት ለችግር የተዳረጉ ደም ስሮችን በማስፋት የተከሰተውን የደም እጥረት ችግር ለመቅረፍ ይሞክራል፡፡ እነዚህ አማራጮች ካልሰሩ ግን አንጎል የሚያስፈልገውን የኦክስጅን አቅርቦት ለማግኘት ስለሚቸገር በርካታ የአንጎል ሴሎች መሞት ይጀምራሉ፡፡
የአንጎል ሴሎች ላይ የሚደርስ ጉዳት ደግሞ እንደ አቶ ግዛቸው የተለያዩ ሰውነት ክፍሎች ላይ አልታዘዝ የማለት ችግር ያስከትላሉ፡፡ በተለይ ደግሞ እጅ እና እግር ዋነኛ ተጎጂዎች ናቸው፡፡ በዚህም የተነሳ አልጋ ቁራኛነትን ያስከትላል፡፡ የሳንባ ምች እና የሰውነት ቆዳ መቆሳሰል ደግሞ የስትሮክ ህመምን ተከትለው ከሚከሰቱ ህመሞች መካከል ተጠቃሽ ናቸው፡፡
ታሞ ከመማቀቅ…
ከላይ ለመግለፅ እንደተሞከረው ስትሮክ መዘዘ ብዙ ህመም ነው፡፡ በድንገት ለሞት እና ለአካል ጉዳት ይዳርጋል፡፡ አስቸጋሪ ባህሪ ያለው ስትሮክ መቼ እንደሚከሰት በትክክል አይታወቅም፡፡ ነገር ግን ስኳር እና የደም ግፊት ህሙማን በማንኛውም ሰዓት ለስትሮክ ሊጋለጡ ይችላሉ፡፡ ስለዚህ የስኳር ህመም እና የደም ግፊት ያለባቸው ሰዎች በማንኛውም ሰዓት ጥንቃቄዎችን ማድረግ አለባቸው፡፡ አመጋገባቸው ላይ ጥንቃቄ ማድረግ አለባቸው፡፡ ከቅባታማ ምግቦች ይልቅ አትክልት እና ፍራፍሬዎችን ማዘውተር፣ አካላዊ እንቅስቃሴን በየዕለቱ ማዘውተር፣ ዓመታዊ የጤና ምርመራን ማድረግ እና ቶሎ ቶሎ ባሞያዎች ማማከር ተገቢ ነው፡፡
በዶ/ር ፋሎስ ሚጋን የተባሉ የህክምና ባለሞያ ደግሞ ንዴት የደም ግፊት ዋነኛ ምንጭ እንደሆነ የደም ግፊት መጨመር ደግሞ በተለይ ወደ አንጎላችን የሚሄደውን የደም ዝውውር በማዛባት ለስትሮክ እንደሚያጋልጡ ይጠቁማሉ፡፡ ስለዚህ ማንኛውም ሰው ስሜቱን የመቆጣጠር ክህሎትን ሊያዳብር እንደሚገባ ይጠቁማሉ፡፡
እንቅልፍ ማጣትን ተከትሎ ወይምን በተደጋጋሚ መናደድ በራሱ ለድብርት ስሜት ሊያጋልጠን ይችላል፡፡ ምክንያቱም ሰዎች ስንናደድ እናዝናለን፡፡ በተደጋጋሚ ስናዝን ደግሞ ቀስ በቀስ ለድብርት ስሜት ልንጋለጥ የምንችልበት እድል ከፍተኛ ነው፡፡ በተመሳሳይ ንዴት ለሌሎች የስነ አዕምሮ ችግሮችም ሊያጋልጠን ይችላል፡፡ ስትሮክ ደግሞ ከእነዚህ ውስጥ አንዱ ነው፡፡ ሲጋራ አለማጨስ፣ የአልኮል መጠጦች አወሳሰዳችንን ጤናማ ማድረግም ይመከራል፡፡ እንግዲህ አቶ ግዛቸውን ጨምሮ ብዙ በድንገተኛው የስትሮክ ህመም ተጠቅተው ለአካል ጉዳት እና ለድንገተኛ ሞት የተጋለጡ ሰዎች ስለስትሮክ ቀድመው የሚያውቁበት አጋጣሚ ቢኖር ኖሮ እነዚህ ጉዳቶች አይፈጠሩም ነበር፡፡ አቶ ግዛቸውም ሀብትና ንብረታቸውን አያጡም ነበር፡፡ ስትሮክ በድንገት ተከስቶ እጅ እና እግራቸውን በማሰር እንዲሁም አንደበታቸውን በመለጎም የሰው እጅ እንዲያዩና የልጆቻቸው ጥገኛ እንዲሆኑ አያደርጋቸውም ነበር፡፡ አገራቸውንም በሞያቸው ብዙ ማገልገል ይችሉ ነበር፡፡ እርሶም በማንኛውም ሰዓት ለዚህ ችግር ሊጋለጡ እንደሚችሉ ያውቃሉ? ካላወቁ ጥንቃቄ ያድርጉ ባለሞ ያዎችንም ያማክሩ፡፡ ካልሆነ ግን ዋጋውን ለመክፈል ይዘጋጁ፡፡S

የነሱ ድፍረት የኛ ፍርሀት ነው –ሉሉ ከበደ (ጋዜጠኛ)

$
0
0

ሙስሊም ወንድሞቻችን ሁለት አመት ለሚጠጋ ጊዜ እየተገደሉ ነው። በጽናት፤ በጀግንነትና በብልሀት እናም በመስዋእትነት የመብት ትግላቸውን ቀጥለዋል። በለተ – አውዳመት ኢድ አልፈጥርም የመስዋእትነት ደማቸውን፤ …ኢትዮያን የተቆጣጠራት የትግራይ ዱር አራዊት መንጋ አፍሷል። የሞቱትን ሁሉ አላህ በጀነት ነፍሳቸውን ያኑር ከማለት በቀር ምን ይባላል ? ለሁሉም ወገኖቻችን ለቤተሰቦቻቸው፤ ለዘመዶቻቸው አላህ ጥናቱን ይስጥ እላለሁ። በከንቱ ለፈሰሰ ደማቸውም እሱ በማያልቅበት ስልጣኑ ፍርዱን ይስጥ። ሳይውል ሳያድር።…አላህ ሁ አክባር!!!
አፋር ለብቻው እየተቀጠቀጠ ሀብቱን ንብረቱን እየተቀማ እየተዘረፈ ነው። ኦሮሞ ለብቻው እየተቀጠቀጠ ሀብቱን ንብረቱን እየተቀማ እየተዘረፈ ነው። ሶማሌ ለብቻው እየተቀጠቀጠ ሀብቱን ንብረቱን እየተቀማ እየተዘረፈ ነው። አማራው እየተቀጠቀጠ ሀብቱን ንብረቱን እየተቀማ እየተዘረፈ ነው። ደቡቡም ቤኔሻንጉሉም…ሁሉም! ድፍን ኢትዮጵያ….
የኢትዮጵያ ሳተላይት ሬዲዮና ቶሌቪዥን ከተመሰረተ ወዲህ፤ ይህ ህዝብ፤ አንዱ ባንዱ ላይ የሚደርሰውን ሰቆቃ መከራና ግፍ ሌላው ሳይሰማ ቀርቶ አይደለም፤ ከዳር እዳር ለአመጽ ያልተነሳው። አንዱ ላንዱ ለመድረስ ሳይፈግ ቀርቶ ሳይሆን፤ አንድ ሆኖ የጋራ ጠላቱን ህውሀትንና የየክልሉን ባንዳዎች አምርሮ የሚታገልበት ድፍረቱ የጠፋው ነው የሚመስለው። ከየቋንቋው ተናጋሪ፤ ዛሬን ኖረን እንሙት ብለው በቆረጡ የጥቅም ምርኮኞች ወያኔ ያዋቀረው የስላላ መረብ፤ የማያፈናፍን በመሆኑም ሊሆን ይችላል ህዝቡ ከየአቅጣጫው መነሳት ያቃተው። የህውሀት ሰላዮች አብዛኛዎቹ የትምህርት ደረጃቸውና የስራ ልምዳቸው የማያስገኝላቸውን ጥቅም ለማግኘት ሲሉ ወገኖቻቸውን አሳልፈው የሚሰጡ፤ ይህ ስልጣን ላይ ያለው ቡድን ንቅንቅ የማይል ነው ብለው የሚያምኑ ናቸው። ህልውናቸውን ከስር አቱ ጋር ስላቆራኙት ተግተው ወገኖቻቸውን ሁሉ ያስበላሉ። ይህ ፍርሀት በያንዳንዱ ሰው ልብ ውስጥ ነግሶ ይሆን ? ከሁሉም በላይ ግን ሁሉንም አንድ ላይ መጨፍለቅ የሚችለው የህዝብ ቁጣ ነው። ለምን ይሆን የዘገየው የኢትዮጵያ ህዝብ ቁጣ ?
Bahir dar 24
መልካሙ ነገር ወያኔ በመላው ኢትዮጵያ ከትግራይ ክፍለሀገር ጨምሮ የጠላቶቹን ቁጥር እያበራከተ መሄዱ ነው ። ይህም በመሆኑ የሚወስደው እርምጃ ሁሉ የውስጥ ፍርሀቱንም ጭምር ይገልጻል። የሚፈራውም አንድ ቀን፤ ከአንድ ጥግ፤ ወይ ከመሀል የሚነሳ የተንቀለቀለ ቁጣ ማእበሉ በሚያስገርም ፍጥነት በመላ ሀገሪቱ ተስፋፍቶ፤ ወያኔ ለወሬ ነጋሪ እንኳ እንዳይተርፍ ሊያደርገው ይችላል። አንባገነኖች አፈናውንና ጭቆናውን እያበዙት በሄዱ ቁጥር፤ የፍርሀታቸውም መጠን እየጨመረ መሄዱ የማይቀር ነው። የፍርሀታቸው መጠን በጨመረ ልክ፤ በህዝብ ላይ የሚፍጽሙትም ግፍ እየከፋ ይሄዳል። በሙስሊም ወንድሞቻችን ላይ የሚያካሂዱት ጭፍጨፋ ይህንኑ ያመለክታል።
ባንድ አጋጣሚ መብቱንና ነጻነቱን ለማይረቡ ደካሞች አሳልፎ የሰጠ ህዝብ፤ በውዴታ ወይም በክብር መልሶ ነጻነቱን ሊያገኝ ከቶም አይቻለውም። በቁጣ እና በሀይል ነው ከጅ ያመለጠ ነጻነት የሚገኘው። በተደራጀ ሀይልና በቆራጥ ትግል ነው ከጅ ያመለጠ ነጻነት የሚገኘው። ወያኔዎች በተቀናጀ የፖሊስና የጦር ሀይል ህዝብን በማሸበር ስራ ላይ ተሰማርተው ህዝቡን አሸባሪ ይሉታል። ህዝቡን እየገደሉት ተገደልን ይላሉ። ባንዲራ ቀደው እያራገቡ ህዝቡን ባንዲራ ቀደደ ይሉታል። ዘጠና ሚሊዮን ህዝብ ይህችን ምድር ትቶላቸው ወዴት እንዲጋዝ አስበዋል? አዎ ይህን ህዝብ አሸንፈውታል። ጥለውታል። ፈሪ ከጣለው ላይ አይነሳም እንዴ?… ፈሪ ግልግል አያውቅም እንዴ? ካንድ መንደር የተውጣጡ ወሮበሎች ይህን ህዝብ በሀይል ጸጥ አድርገው እየገዙ እንድሚዘልቁ አምነዋል? እኛስ እየተረገጥን ተገዝተን መኖር እንዳለብን አምነን ተቀብለናል?
ምን ጊዜም የአንባገነኖች ብርታትና ጥንካሬ የህዝብ ፍርሀትና መንበርከክ ነው። የኛ ችግር ደግሞ ከፍተኛ ፍርሀት በልባቸው ውስጥ መኖሩን አውቀን መድፈር አለመቻላችን ነው። እነሱ ይህን ስልጣን ተነጥቀው በጃቸው ያስገቡትን የሀገሪቱን ሀብት እንዳያጡ ይፈራሉ። እኛ ደሞ ከሞቱት በላይ ከነሱ በታች አድርጋ የምታኖረንን ኩርማን እንጀራ እንዳናጣ እንፈራለን። እየፈራንም ድንገት ባላሰብነው ሁኔታ ያቺን የምንፈራላትንም ጥቅም አሳጥተውን እንደምንወድቅ አሳይተውናል። ስንት ሺ ህዝብ ነው በማያውቀው ምክንያት ከስራ የሚባረረው? ብረት የተሸከመው መለዮ ለባሽ ሳይቀር ስንቱ ሺ ስንት ጊዜ ከሰራዊቱ ተባረረ? መፍራቱ፤ አቤት ወዴት እያለ ለነሱ መታዘዙ፤ በኢትዮጵያ ውስጥ ለኑሮና ለህይወት ዋስትና ነው ብሎ የሚያምን ይኖር ይሆን?
ሀይሌ ገብረስላሴ እግራቸው ስር የወደቀው ፕሬዚደንት እሆናለሁ እያለ መለፍለፍ የጀመረው ሀብቱን ንብረቱን ሊዘርፉት እንደሚችሉ ጠንቅቆ በመረዳቱ ይመስላል። የሚወደውን የኢትዮጵያ ህዝብ ጠልቶ አይመስለኝም እነሱ ስር መለጠፍ የፈለገው። ጨካኝ ወንጀለኞች መሆናቸው አስፈርቶት ነው። ስልጣኑ አይደለም አንባገነኖችን ጨካኝና ጨፍጫፊ የሚያደርጋቸው። ጥቅሙ ነው። ያን ጥቅም የማጣት ፍርሀት ነው ክፉ የሚያደርጋቸው ። ጥቅሙ የሚገኘው ስልጣኑን ተከትሎ ነውና።
muslim1የሰው ልጅ በተፈጥሮው የሚገባውን ሰባዊ መብት አላውቅም፤ አልቀበልም፤ አላከብርም፤ ብሎ በህዝብ ላይ ያሻውን እየፈጸመ ለመኖር የቆረጠ የህገወጦች ቡድን ሁሉን በተቆጣጠረበት አገር ውስጥ፤ እርግጥ ፍርሀት የህብረተሰብ የለትተለት ህይወት ሊሆን ይችላል ። እንዳንታሰር መፍራት፤ እንዳንገደል መፍራት፤ በእስር ቤት የቁምስቃይ እንዳይደርስብን መፍራት፤ ልጄን ወንድሜን ይገሉብኛል ብለን መፍራት፤ ስራዬን አጣለሁ ብለን መፍራት፤ ያለኝን ሀብት ነጥቀው ያደኽዩኛል ብለን መፍራት፤ አዎ ባሁኑ ጊዜ ኢትዮጵያ ውስጥ ይህ መሰረት ያለው ፍርሀት ነው። አንካካድም። እንዲህም ሆኖ ግን የሚደርስባቸውን ሁሉ እያወቁ፤ ለህይወታቸውም ለንብረታቸውም ቅንጣት ሳይሳሱ፤ በግላቸው ለመጠቀም ሳይሆን፤ ኢትዮጵያውያን መብት ነጻነትና ዲሞክራሲ ያስፈልገናል ብለው፤ እነእስክንድር ነጋ፤ እነ አንዷለም አራጌ፤ ወያኔ እስር ቤት የታጎሩት የነጻነት ታጋዮች በሙሉ፤ የሙስሊም ወንድሞቻችን መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ አባላት ብሎም መላው ኢትዮጵያዊ ሙስሊም በሙሉ፤ ድምጻቸውን ከፍ አድርገው እየጮሁ ይህን የነፍሰገዳዮች ቡድን ሲሞግቱ፤ አብሮ ለመነሳትና ለመከተል ወኔ ማጣታችን ነው ከሁሉም የከፋ ፍርሀት። የመጣው ይምጣ ብሎ ጀግና ተነስቶ ይህን አራዊት ቡድን ሲጋፈጥ እያዩ ቶሎ ተነስቶ ከጎኑ መቆም ያለመቻል ነው አደገኛው ፍርሀት።
የቱኒዚያው ለውጥ የመጣው አንድ ወጣት እራሱን በማቃጠሉ፤ ከዳር እስከዳር የሀገሪቱ ሰው ሁሉ ተነቃንቆ፤ በጥቂት ቀናት ነገሩን ሁሉ ቀየረው። በኢትዮጵያ ውስጥ ጀግናው የኔ ሰው ገብሬ ለፍትህ ሲል ራሱን አቃጠለ። ወያኔ በህዝቡ ላይ የጫነው የፍርሀት ድባብ በልጦ ነው መሰለኝ የተንቀሳቀሰ ሰው አልታየም።
በማናቸውም ስርአት ውስጥ ኢትዮጵያ ጭቆናን፤ አንባገነንነትን፤ ዘረኝነትን፤ የሚቃወሙ ጀግኖች ሞልተዋታል። ቀድመውን የተነሱትን ፈጥኖ የመከተል ወኔ ነው የጎደለን። ሰማያዊ ፓርቲ አዲስ አበባ ውስጥ በቅርቡ በጠራው የተቃውሞ ሰልፍ ላይ ከሶስት መቶ ሺህ ህዝብ ያላነሰ ወቷል። የቀረው እቤት ውስጥ ምን ያደርግ ነበር ?.. ሙስሊም ወንድሞቻችን ሁለተኛ አመታቸውን ይዘዋል ድምጻችን ይሰማ፤ የሀይማኖት ነጻነታችን ይከበር፤ ህገመንግስቱ ይከበር እያሉ ሲጮሁ፤ ሲገደሉ፤ ክርስቲያኑ ምን እያደረገ ነው ? እስላም መንግስት ሊሆንብህ ነው ብሎ ወያኔ የሚያወራው ውሸት ለኢትዮጵያዊው ክርስቲያን የመዝናኛ የመሳቂያ ቀልድ ነው። ከወንድሞቹ ጋር መነሳት ያቃተው፤ ለራሱ ነፍሱ በፍርሀት ብትቀጥን ነው እንጂ። ( በነገራችን ላይ ኢትዮጵያ ውስጥ ሰዎች ሲደብራቸው ወያኔ ዛሬ ምን ውሸት አወራ? ቴሌቪዥን ያየ አለ? ማለት በየቤቱ የተለመደ ሆኗል ይባላል) እርግጥ የሀገር ቤቷ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን በወያኔ ተማርካለች፤ የሀይማኖት መሪዎች፤ የወያኔ ባንዳና ቅጥረኞች ሆነዋል። የሙስሊሙን ቅጥረኛ መጅሊስ ምእመኑ እንቢ እንዳለ፤ የክርስቲያኑም ምእመን ያንኑ አቁዋም ይዞ ከወንድሞቹ ጎን መታየት ነበረበት። በሙስሊም ወንድሞቹ ላይ እየደረሰ ያለው ግፍ ኢትዮጵያዊውን ክርስቲያን እያሳመመው እያንገበገበው ነው። ይሄ ምንም የሚያጠራጥር ነገር የለውም። ሙስሊሙ በየመስጊዱ ያደረገውን ክርስቲያኑ በየ ቤተክርስቲያኑ ለማድረግ ግን ዘግይቷል። ጊዜ ግን ምንጊዜም አለ። ኢትዮጵያውያን ክርስቲያኖችም ተነሱ!
ዊንስተን ቸርችል ተናገሩት ተብሎ ከተጻፈ ጥቅስ እንዲህ የሚል አየሁ “….ታያላችሁ እነዚያን በተደላደለ መሰረት ላይ ተደላድለው የተቀመጡ አንባገነኖች? በወታደሮቻቸው አፈሙዝ ተከበው፤ በፖሊሶቻቸው ቆመጥ ተከበው….ግን በልባቸው ውስጥ ለመግለጽ አዳጋች የሆነ ፍርሀት አለባቸው። …መልካም አስተሳሰቦችን ይፈራሉ። ጠንካራ ቃላትን ሳይቀር ይፈራሉ። ስለ ስርአታቸው ስለሁኔታቸው ከውጭ የሚወሩ ነገሮችን ይፈራሉ። በሀገር ውስጥ የሚንሸራሻሩ ትክክለኛ ሀሳቦችን ይፈራሉ። ስለሚያስፈሯቸውም ሀሳቦችን ያግዳሉ። ያፍናሉ። ሰው ሀሳቡን እንዳይገልጽም ይከለክላሉ። እነሱ ከሚያስቡት የተለየ ኢምንት አስተሳስብ በሀገር ውስጥ ሲንቀሳቀስ ካዩ በፍርሀት በድንጋጤ ይርዳሉ….”
የህውሀት ሰዎች የኢትዮጵያን ህዝብ ለማፈን የሚደክሙት ለምንድነው? የሽብርተኛ ህግ አውጥተው የሚቃወማቸውን ሁሉ፤ ጋዜጠኛውን ሁሉ እስር ቤት የሰበሰቡትና ድፍን ያገሪቱ ህዝብ እነሱ የሚዋሹትን እንጂ እንዳይሰማ ለማድረግ ባለመታከት የሚጥሩት ለምንድነው? መልሱ ከላይ ዊንስተን ቸርችል ከተናገሩት ውስጥ አለ። እኛ የተጎዳነው ፈሪዎች መሆናቸውን ማወቅ አቅቶን ደፍረን እነሱን ለማንበርከክ አለመተጋገዛችንና አለመነሳታችን ነው።
ከደቡብ አፍሪካው አፓርታይድ ጋር ይፋለም የነበረው የነማንዴላ ድርጅት እንደ አወሮፓውያኑ ዘመን አቆጣጠር በ1949 ዓም ላይ አመታዊ ጉባኤውን ሲያካሂድ ህዝቡን በማንቀሳቀስ ተግባራዊ የሚሆን የሰላማዊ ትግል እርምጃዎችን አቅዶ ነበር። እነዚያም እቅዶች ቦይኮት፤ የስራማቆም አድማ፤ እቤት የመዋል አድማ፤ ከመንግስት ጋር ያለመተባበር፤ ዘረኛ ለሆኑ ህጎች ያለመገዛት፤ ባጠቃላይ ሀይል ያልተቀላቀለበት አመጽ፤ እንቢታ የመሳሰሉት ነበሩ።
በ1951 መጨረሻ ላይ ይህንኑ የትግል ስልት በተግባር ሊጀምሩ፤ የኤ-ኤን-ሲ መሪዎች ተሰበሰቡና አግባብነት የሌለውንና አፓርታይድ ህዝቡን ለማፈን ያወጣውን ህግ ባደባባይ ጥሰው በማሳየት፤ ለመታሰር የሚፈልጉ በጎ ፍቃደኞችን ማሰባሰብ ቀጠሉ። በሀገራችን ወያኔ እንደሚጠቀምበት የሽብረተኛ ህግ ማለት ነው። በ1952 መጀመሪያ ላይ ወደተግባር ሲሻገሩ በበጎ ፍቃደኝነት ህግ ጥሰው ለመታሰር የወሰኑ በርካታ ሰዎች ተሰለፉና ነጮች ብቻ መዘዋወር የሚችሉበት አካባቢ ጥሰው መግባት፤ ለጥቁሮች ያልተፈቀዱ ሁቴሎችና መዝናኛዎች ጥሰው መግባት፤ ለነጮች ብቻ በተፈቀደ የማመላለሻ አውቶብሶችና ባቡሮች ላይ ሆ ብለው መግባት፤ ለጥቁሮች ከተፈቀደ ሰአት ውጭ ማምሸት ተግባር ላይ እያዋሉ ሆን ብለው በብዛት ወደ እስር ቤት ይገቡ ጀመር። ይህ የመጀመሪያው የእንቅስቃሴ ክፍል ሲሆን በሁለተና ደረጃ የተነደፈው በመላ ሀገሪቱ ባንድ ጊዜ አንድ አይነት ሰላማዊ እርምጃ መውሰድ ነበር። ያም ብሄራዊ እንቢተኝነትና ብሄራዊ የስራ ማቆም አድማዎች ነበሩ።
ጁን 26 1952 ህግን የመጣስ ተቃውሞ በያለበት ተጀመረ። ህዝቡ በነቂስ ወቶ በጎ ፍቃደኞቹን እያበረታታና እየዘመረ ድጋፉን ሰጠ። ጥቁሮች እንዳይደርሱ በህግ የተከለከሉባቸውን ቦታዎች እየጣሱ በሀይል በመግባት በጅምላ ወደ እስር ቤት መጋዝ ጀመሩ። በርካታ የኤ-ኤን-ሲ መሪዎችም ቡድኖችን እየመሩ አብረው ታሰሩ። ፖሊስ ያሰረውን ህዝብ በሙሉ ፍርድ ቤት እያመላለሰ በመክሰስ ስራ ላይ ተጠመደ። “ሁላችንንም እሰሩን” እያለ ህዝቡ፤ “ማንታስሮ ማን ይቀራል” እያለ፤ በፉክክር መንግስቱን ፈተና ላይ ይጥለው ጀመር። በመጀመሪያዋ የአመጽ እለት 250 በላይ በጎ ፍቃደኞች ህግ ጥሰው ታሰሩ። በተካታታይ በተካሄደ የአምስት ወር ዘመቻ 8500 ሰዎች በበጎ ፍቃድ ህግ የመጣስ ዘመቻ ተካፍለው እስር ቤት ገቡ። የህክምና ዶክተሮች፤ የህግ ጠበቃዎች፤ የፋብሪካ ሰራተኞች፤ የዩኒቭርስቲ መምህራንና ተማሪዎች ባጠቃላይ ከሁሉም የህብረተሰብ ክፍል ፍጹም ወደር በሌለው አንድነትና መተባበር ያንን መንግስት እስከመጨረሻ ሊታገሱት እንደማይችሉ አረጋገጡለት። ህዝቡ ይዘምር ነበር የባለስልጣናቱን ስም እየጠራ “ ክፈቱት.. ክፈቱት በሩን፤ የእስር ቤቱን…እንፈልጋለን መግባቱን..” እያለ።ይህን ህዝባዊ ሰላማዊ አመጽ ያቀደውና የመራው የማንዴላ ድርጅት ኤ-ኤን-ሲ በህዝቡ ዘንድ እጅግ ትብብርና ድጋፍ በማግኘቱ፤ ባንድ ጊዜ የአባላቱ ቁጥር ከ20‹000 ወደ 100‹ 000 ተተኮሰ።
ከዚያ በፊት የደቡብ አፍሪካ ህዝብ በዘረኞቹ ገዢዎች አንጻር፤ አንድ መሆኑን ያረጋገጠበት አጋጣሚ ነበር። ነሀሴ 1943 ዓም ላይ ንብረትነቱ የነጮች የሆነ የህዝብ ማመላለሻ አውቶቡስ ኩባንያ የአውቶብስ አገልግሎት ዋጋ ከአራት ሳንቲም አንድ ሳንቲም ጨምሮ ከፍ አደረገ። እነማንዴላ ህዝቡ ባውቶብሶቹ እንዳይሳፈር አድማ ጠሩ ( ቦይኮት ) ዘጠኝ ቀን አውቶብቹ ሰው የሚባል አጠገባቸው አልደርስ አለ። ኩባንያው ተሽመድምዶ ቁጭ አለ። ጠባቂውና ተንከባካቢው ዘረኛው የነጮች መንግስት ህዝቡን ደብድቦ ባውቶሶቹ እንዲገለገሉ ማድረግ አልቻለም። ዘሮቹን አጽናንቶ ከባጀቱ ለኪሳራው ማካካሻ ከመስጠት በቀር። የህዝቡን መቁረጥ የተረዳው ኩባንያ መጀመሪያ በሚያስከፍለው አራት ሳንቲም ስራውን ቀጠለ። አገልግሎቱን ለመስጠት ተገደደ። ህዝብ እንዲህ ለአንድ አላማ በአንድ ድምጽ በአንድ አቋም ጸንቶ እርምጃ ከወሰደ፡ ካልተንጠባጠበ፤ ማናቸውንም የአመጸኞች ስርአት የማንበርከክ ሀይል አለው። አንድ መሆን ያቃተው ህዝብ ግን ዝንተአለም እየተረገጠ ሲገዛ ይኖራል።

ኢትዮጵያን ዳግም በልጆቿ አንድነት ተነሳለች!
ሞት ለወያኔ
lkebede10@gmail.com

ከሦስት ጊዜ በላይ የሞተ ብቸኛው ዝነኛ የሀገር መሪ

$
0
0

ይሄይስ አእምሮ

ወቅቱ በኦርቶዶክሳውያንና በኢትዮጵያውያን ካቶሊኮች ዘንድ የፍልሰታ ለማርያም የፆምና የሱባኤ ጊዜ ነው፡፡ በዚህ ለየት ባለ የሱባኤ ወቅት ለምንገኝ ወገኖች ፈጣሪ የልባችንን መሻት ተረድቶ የዘመናት ህልማችንን በቅርብ እውን ያድርግልን፤ የሚሳነው ነገር የለምና፡፡ ጸሎት ምህላችንን ሰምቶ ከነዚህ ሽል መንጣሪዎች፣ ከነዚህ የሰው ግርድ እና አመሳሶ አውጪዎች ይገላግለን፡፡ የእስላም የክርስቲያኑን ዕንባ ተመልክቶ ከነዚህ ሰው በላዎች ነጻ የምንወጣበትን መንገድ ያሳየን፡፡ በመካከላችን የቆመ የሚመስለውን ጽልመተ መንጦላዕት ይበጣጥስልንና ወያኔ የዘራውን የልዩነት አዝርዕት ሁሉ ይመነቃቅርልን፡፡

ሰው ስንት ጊዜ ይሞታል? ብለን ብንጠይቅ እንደየአመለካከታችን የተለያዩ መልሶችን የምናገኝ ይመስለኛል፡፡ የመልሶቻችን መለያየት መሠረትም ለሞት ያለን ግምትና የምንሰጠው ፍቺ ነው፡፡ ከዚህ አንጻር ‹መለስ ዜናዊ ስንት ጊዜ ሞተ?› ለሚለው ጥያቄ መልስ እኔን ጨምሮ ብዙዎች የሚቃወሙት ሰዎች ከሦስት ጊዜ በላይ እንደሆነ ቢናገሩ እንደአካሄድ ትክክል ናቸው፡፡ እመለስበታለሁ፡፡

melesአንዲት ማሳሰቢያ ቢጤ ጣል ባደርግ ደስ ይለኛል፡፡ ይህን ጽሑፍ ሃይማኖት የሌለው ሰው፣ በ‹paranormal and/or parapsychology› ኅልውና የማያምን ሰው፣ እምቦቀቅላው ሣይንስ አምስቱን የስሜት ሕዋሳት ብቻ ተመርኩዞ ከሚሰጠው መረጃ ውጪ ሌላ ሃሳብ የማይቀበል ዝግ ሰው እንዳያነብ እመክራለሁ፡፡ (የቅንፍ ሰበር ሃሳብ! በሞስኮ ኦሎምክ የ1500ኪ.ሜ ሩጫ አሁን እየተካሄደ ነው – ልክ አሁን፡፡ መጻፌን ቆም አድርጌ ይህችን አጭር ሩጫ ጨረስኳት፡፡ በውጤቱ ግን አዘንኩ – ወልዶ ለሰው መገበር የማይሰለቻት ሀገራችንም አሳዘነችኝ፡፡ ይህን ሩጫ በአንደኛነት ያሸነፈችው ‹ስዊድናዊት› አበባ አረጋዊም አሳዘነችኝ፡፡ በዚህ ውድድር 8ኛ ሆና የጨረሰችው ተወዳዳሪ ገንዘቤ ዲባባም በሀገሯ ልጅ በ‹ስዊድናዊቷ› አበባ አረጋዊ በሰፊ ልዩነት መሸነፏም አስተከዘኝ፡፡ አበባ ድሏን ለ‹ዜጎቿ› ለመግለጽ ባንዲራየ ብላ የያዘችውን የስዊድን ሰንደቅ ዓላማ ስታውለበልብ የተሰማኝ ስሜትም የተለዬ ነው – የሰው ወርቅ ላያደምቅ ዘመን በፈጠረው የኢትዮጵያውያን ተከፍሎ ሊያልቅ ያልቻለ የትውልድ ዕዳ ምክንያት ዜጎቻችን ከችግርና ከፍትህ አልባ መንግሥታዊ አሠራር ለማምለጥ ሲሉ የገቡበትን የሥነ ልቦናና የፖለቲካ ቀውስ በዚህ አጋጣሚ ሳስበውና ከስድስት ወራት ገደማ በፊት በተሰጣት የሁለትዮሽ ጠቀሜታ ባለው ዜግነት ምክንያት አበባ ሌላ ባንዲራ ስታውለበልብ ሳያት በእውነቱ ጥልቅ የሀዘን ስሜት ተሰማኝ፡፡ መቼ ይሆን ሀገራችን የወላድ መካንነቷ የሚያቆመው? በነገራችን ላይ የአበባ ችግር በሀገራችን ከነገሠው የዘረኝነት ልክፍት ጋር እንደማይገናኝ የታወቀ ነው – ምክንያቱም ልጂቷ ትግሬ በመሆኗ በዚያ በኩል የትግሬው መንግሥት ሊታማ እንደማይችል እረዳለሁ፡፡ ችግሩ ሌላ መሆኑ ሲወራ ሰምቻለሁ፡፡ ለነገሩ በስፖርቱ መንደርም የጎሣው ተዋፅዖ ትልቁ የድቀታችን መንስኤ መሆኑን አንረሳም፡፡)

ወደቀደመው ነገራችን እንግባ፡፡ ፍቼ አካባቢ የተፈጸመ እውነተኛ ታሪክ ላስታውሳችሁ፡፡ ጊዜው ራቅ ይላል – ግን በደርግ ዘመን ነው፡፡ አንዲት ተማሪ በጠና ትታመማለች፡፡ ያን ተከትሎም ለህክምና ወደ አዲስ አበባ ትወሰዳለች፡፡ በህክምና ብዙ ብትረዳም ሕይወቷ ሊተርፍ አልቻለም፡፡ አስከሬን ለቀብር ወደፍቼ ይመለሳል፡፡ መምህራን፣ ተማሪዎች፣ ቤተሰብና የአካባቢው ሕዝብ በተገኙበት የቀብር ሥነ ሥርዓቷ ሊፈጸም ሲል አንድ አስደናቂ ነገር ይከሰታል፡፡ ካህኑ ጸሎታቸውን ጨርሰው ሣጥኑ ወደተዘጋጀው ጉድጓድ ሊገባ ተሸካሚ ሰዎች ሲጠጉ ሬሣው ከውስጥ መንቀሳቀስ ይጀምራል፡፡ ከሞተች ከሦስት ቀናት በላይ የሆናት፣ በፎርማሊንና በልዩ ልዩ ሕክምናዊ መነካካት ከሬሣነት ተራ የወጣው የዚያች ተማሪ አስከሬን ሲከፈት ተማሪዋ ቁጭ ትላለች፡፡ ቀባሪዎች ይደነግጣሉ፡፡ ሁሉም በሽብርና በጭንቀት ይዋጣል፡፡ የደፈሩ ሰዎች ልብስ ያለብሷታል፤ ካህናትም ያናግሯታል፡፡ ተመልሳ ጤናማ ትሆንና ንግግርም ትጀምራለች፤ የተናገረችው ግን ‹ንስሃ ግቡ! ኃጢኣት አትስሩ› የሚል ብቻ ይሆናል፡፡ ‹ሌላ ነገር እንድናገር አልተፈቀደልኝም›በማለትም ቁርጡን ታሳውቃለች – ይጎርፉላት የጀመሩትን በርካታ ጥያቄዎች ለማስቆም፡፡

እንደተረጋጋች – ባለፉ ቀናት ያስተናገደቻቸውን የተዘበራረቁ የሥጋ፣ የነፍስና የመንፈሳዊ ሕይወቶች መስመር ከያዙላት በኋላ ወደ ትምህርት ቤቷ ተመልሳ በህመሟና በሞቷ ምክንያት ተቋርጦ የነበረውን ትምህርቷን ለመቀጠል ወደ ክፍል ትገባለች፡፡ ነገር ግን እርሷ ክፍል ገብታ ከመቀመጧ የክፍል ተማሪው ከክፍል ውልቅ ይልና ብቻዋን ትቀራለች፤ ምክንያቱም ተማሪዎች ያን ያልተለመደና አስደንጋጭ የ‹ከሞት በኋላ ሕይወት› አያውቁም ነበርና፡፡ በዚያም ሳቢያ ከክስተቱ ጋር በቀላሉ መለማመድ ስላቃታቸው የነበረው ብቸኛ አማራጭ ‹ሟች›ን ወደሌላ አካባቢ ወስዶ ማስተማር ነበርና እንዲያ ተደረገና ሕይወት ቀጠለች፡፡… እንዲህ ዓይነት ነገር በኢትዮጵያም በሌሎች ሀገሮችም በብዛት ባይሆንም እጅግ አልፎ አልፎ ይከሰታል፡፡ ማመን አለማመን የየራስ ድርሻ ነው፡፡

ካልሰለቻችሁ አንድ ልጨምር መሰለኝ፡፡ አንድ ሰው ለመስክ ሥራ ወደ ደቡብ ኢትዮጵያ ይሄዳል፡፡ በሄደበት አካባቢ በቢጫ ወባ ይነደፋል፡፡ ወባዋ ለህክምናም ለታማሚም አስቸጋሪ እንደመሆኗ – በተለይ የተወሰነ ጊዜ ካለፈና በሰውነት ውስጥ ከተራባች  በኋላ – ጭንቅላቱ ውስጥ እንደገባችና እንደማይተርፍ ቤተሰቦቹ ሲነገራቸው ከክፍለ ሀገር ሆስፒታል ወደ አዲስ አበባ ያመጡታል፡፡ የሕክምና ዶክተር ጓደኛው ወደሚሠራበት አንድ የመንግሥት ሆስፒታልም ያስገቡታል፡፡ ያ ጓደኛው ከረዳቶቹ ጋር ጓደኛዊና ሙያዊ ልዩ ክብካቤውን ሲያደርግለት ውሎ ለተረኛው ዶክተርም ‹አደራህን፣ ዘመዴ ነው፤ በተቻለህ ሁሉ ርዳው፣ አንድ ነገር ቢከሰትም ቢሆንም እንኳን እኔ ሳልመጣ ወደሬሣ ክፍል እንዳትልከው እባክህን› በማለት የመዳን ተስፋ የሌለው መሆኑን ግን በልቦናው ተገንዝቦ ወደቤቱ ይሄዳል፡፡

ያ ጓደኛ የጠረጠረው አልቀረም፡፡ ጓደኛ ዶክተር ልብሱን ለውጦ ምናልባትም የሆስፒታሉን ዋና በር ብዙም ከመራቁ ሰውዬው ይሞታል፡፡ እስትንፋሱ ስለመቆሙና ስለመሞቱም የህክምና ሙያዊ ፍተሻ  ከተደረገ በኋላ የጓደኛውን ቃል ለማክበር ያልቻለው ተረኛ ዶክተር የሟችን ሬሣ ወደአስከሬን ክፍል ለክፈና ይልከዋል፡፡ በዚያም ከመሰል አስከሬኖች ጋር እንዲያድር አንዱ ፍርጎ ይሰጠዋል፡፡

በማግሥቱ የሬሣ ክፍል ሠራተኛው ሲገባ ግን ያ በቢጫ ወባ ሞተ የተባለ ሰውዬ መግነዙን ፈትቶ፣ የተተበተበበትን እሥራት ለመፍታት ባደረገው ጥረትም ፊቱን ቦጫጭሮ  ቁጭ ብሎ ይገኛል፡፡ ነፍሱ ከሥጋው ተለይታ በእነማንና በምን ሁኔታ የት ደርሶም ለምን እንደተመለሰ ዝርዝሩ ብዙ ነውና ለአሁኑ አስፈላጊያችን ባለመሆኑ ይቅር፡፡ ግን ሰው በሥጋው ከሞተ በኋላም ሊመለስ እንደሚችልና ሌላ የመሞቻ ቀኑን የሚጠብቅ መሆኑን መረዳት የሚገባ መሆኑን አስምሬበት ልለፍ፡፡ ዓለማችን ብዙ ከአእምሮ በላይ የሆኑ ክንውኖችና ተዓምራት ቤተሙከራ ናት፡፡ ሣይንስ ደግሞ በዳዴ ደረጃ የሚገኝ ሕጻን ነው፡፡

በእማሬያዊ ትርጉም ሞት ማለት የነፍስና የሥጋ መለያየትና አንድ ሰው ከምድራዊ ሕይወት የሚሰናበትበት ሂደት ነው፡፡ በፍካሬያዊ ትርጉም ደግሞ አንድ ሰው በሕይወት እያለም ሆነ ከሞተ በኋላ በክፉ ሥራው ዘወትር ስሙ የሚወሳና ወደዚህች ምድር የመምጣቱ ምሥጢር ለዜጎች መሰቃየትና መበደል ከሆነ የሞት ሞት የሞተ ያህል ተቆጥሮ በታሪክና በትውልድ የሚኮነን ሆኖ በክፉ እየተዘከረ ይኖራል – ያም ከዋና አካላዊ ሞት በበለጠ እንደትልቅ ሞት ይታሰባልና ብዙዎች ሲሸሹት ይስተዋላል፡፡ አንዳንዶች ግን የክፋት ዕቅድና ትልማቸው እስከሰመረላቸው ድረስ ለዚህ ዓይነቱ ሞት ደንታ የላቸውም፡፡ ከዚህ አንጻር ዓለማችን የብዙ ባለመጥፎ ታሪክ ሰዎች ሥፍራ ስለሆነች ምሳሌ ለመጥቀስ የማንቸገርበት ጊዜ ላይ እንገኛለን፡፡ እንዲያውም በተቃራኒው በዘመናችን ጥሩ ሰው የማጣት ችግር እንጂ በጥባጭ የማጣት ችግር የለብንም፡፡ ዛሬ ዛሬማ ስሙን በክፋት መዝገብ ለማስከተብ የሚሯሯጠው የዓለም ዜጋ በጣም እየበዛ ነው፡፡

መለስ ዜናዊ በአካላዊ ሞት በትንሹ ሁለት ጊዜ ሞቷል፡፡ አንደኛው በኢሳት ቴሌቪዥን ቀድሞ የተገለጠው የሐምሌ 7 ቀን 2004 ዓ.ም በውስጥ ዐዋቂዎች ዘንድ እውነተኛ የሚባለው ሞቱ ሲሆን ሁለተኛው በኢቲቪ የተገለጠው የነሐሴ 15 ቀን 2004 ዓ.ም ሞቱ ነው፡፡ እንደዚህ ዓይነት ሁለት ሞቶችን የተጎናጸፈ ብቸኛው የሀገርና የአንድ ብሔር መሪ ቢኖር መለስ ዜናዊ ነው፡፡ ሁለቴ መሞት የሚቀናበት ከሆነ በርግጥም ያስቀናል፡፡ የሁለቱ ሞቶቹ የጊዜ ልዩነት ደግሞ ቀላል አይደለም – የአንድ ድፍን ወርና የስምንት ወይ የሰባት ቀናት ልዩነት ማለት በመካከሉ የሚሊዮኖች ዜጎች ሞት ወይ ልደትና ሠርግ የሚከናወንበት ረጂም ጊዜ ነው፡፡ የዚህ ልዩነት መፈጠር ምክንያት በወቅቱ በወያኔዎቹ በራሳቸውና ሪፖርተርንና አዲስ አድማስን በመሰሉ በወያኔያውያንና አሽቃባጭ ሚዲያዎች እንደተገለጠው  መለስ ዜናዊ ከበሽታው አገግሞ ወደቢሮው ለመግባት ሰውነቱን እያሟሟቀ ወይም በቤተ መንግሥት እልፍኝ ውስጥ ተቀምጦ ሱዳናውያኑን እያስታረቀ ሳይሆን ሞቱ ዱብ ዕዳ ስለነበር ቤታቸውን ለሀዘን አስተካክለው እስኪገኙ ድረስ ጊዜ ለመግዛት እንደነበረ ተረድተናል – አለበለዚያ ሌሊት ሞቶ ጧት ተነግሮ ወዲያውኑ ያ ሁሉ በብዙ ሺዎች የሚገመት ከናቴራና ኮፍያ ተሠርቶ ሊሠራጭና ቀድሞ በአባላት የተዘጋጀው ሀዘን ከመቅጽበት ተግባራዊ ሊሆን ባልቻለ ነበር (‹ጧት ተመርቶ ከሰዓት መርካቶ› ለ‹ላቭሊ› በስኩት የተሠራ ማስታወቂያ እንጂ ከዚህ በመኮረጅ ‹ሌሊት መለስ ሞቶ ጧት በምስሉ ከናቴራ ተሰፍቶ› ቢባል ግነቱ የዚያኛውን ያህል አይጥምም ብቻ ሣይሆን ማስታወቂያውን የሠሩትን እነበረከትንና ሽመልስ ከማልን ትዝብት ውስጥ ይጥላል – ትዝብት እሚባል ነገር አያውቁም እንጂ ደግነቱ) ፡፡ ያን ዓይነት ብልግና የተሞላበትና ከባህልም ከሃይማኖትም ከሞራልም ማዕቀፎች የወጣ  የሞተን ሰው ‹ሥራ ላይ ነው፤ ሽርሽር ላይ ነው፤ ኢሳት የፈጠራ ወሬ ነው ያወራው…› በማለት በእግዜር እጅ የተያዘ ሙት ሰው ላይ የማሾፍና የመቀለድ የቦዘኔ ሥራ መሥራትን የመረጡት እውነቱ መውጣቱ የሚቀር መስሏቸው ሣይሆን መራሩ መፃኢ ዕድላቸው አስጨንቋቸው ነው፡፡ ሰው መቼም ወዶ አንድን ሰው ሁለቴ አይገድልም፡፡ ወያኔዎች የሚያደርጉትን አያውቁም ነበር – አሁንም አያውቁም፡፡ የሸሹት እውነት ሮጦ ያዛቸውና የዛሬ ዓመት በዚህ ወቅት ገደማ የአናኮንዳውና ኮብራው ወያኔ መርዛማ ጭንቅላት ከእናት የዘንዶ ሰውነት መበጠሱን ሳይወዱ በግዳቸው ዐወጁ፡፡ ከዚያን ጊዜ በኋላም ቆሌ ርቋቸው ይሄውና የፈጣሪ ፍርድ እውን እስክትሆን በስቃይና በጣር ላይ ይገኛሉ፡፡ ፍርዱ ትክክል የሆነው እግዚአብሔር ደግሞ ሰዓቷን ጠብቆ ሁሉንም የሥራቸውን እንደሚሰጣቸው የታመነ ነው፡፡ የውሻን ደም በከንቱ የማያስቀረው የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር የተመሰገነ ይሁን፡፡

 

ይህችን የ2005ዓ.ም ፍልሰታ ብዙዎቻችን ተስፋ ጥለንባታል፡፡ በድረ ገፆች በቅርቡ ባነበብነውና ከበፊትም አንዳንዶቻችን ከአባቶች በሰማነው የትንቢት ቃል መሠረት  የኢትዮጵያ የዕዳ ደብዳቤ የሚቀደድበትና ሰላም በሀገራችን የሚሠፍንበት ዘመን እየመጣ እንደሆነ አምነን ጸሎታችንን እያቀረብን እንገኛለን፡፡ እግዚአብሔር ዐመፀኞችን እንደሚቀጣ ደግሞ ከጥንትም የታወቀ ነውና ብዙ ወደተገፋነው ኢትዮጵያውያን ፈጣሪ ፊቱን እንደሚመልስልን በሙሉ ልብ እናምናለን፡፡ ይሆንልናል ብለን ካመንን ይሆንልናልና ተስፋችንን በርሱው እናድርግ ወገኖቼ፡፡ የእርሱ ፍርድ ደግሞ ይዘገያል እንጂ አይቀርም፡፡ ፍርዱ የሚዘገይ ወይም የሚቀር የሚመስላቸው ግን በሞኝነት ላይ ሞኝነትን እየደረቡ ለከፋ መለኮታዊ ቅጣት ይዳረጋሉ፡፡ ማንም ቢሆን የእጁን እንደማያጣ በመዘንጋትም አምላክን ይፈታተናሉ፡፡

ባጭሩ ለመከለስ ያህል ወያኔዎች የሚጠፉበትና ከነሰንኮፋቸው ተነቅለው የሚጣሉበት ምክንያት ብዙ ቢሆንም የተወሰኑትን ቀጥለን እናስታውሳለን፡፡

እስከዚህን ዘመን ባልታወቀ አዲስ አስተሳሰብ ተመርተው ሀገሪቱን በዘርና በቋንቋ ከፋፍለዋል፤ ይህም ነገር ዜጎችን በተወሰነ ደረጃ አናቁሯል፤ ትዳርን እስከመበተንና ፖለቲካን አልጋ ውስጥ አምጥቶ እስከመነታክና እስከመጋደልም አድርሷል፡፡

ኢትዮጵያን ያለወደብ አስቀርተዋል፤ ለተባበሩት መንግሥታትም ደብዳቤ በመጻፍ በየትም የዓለም ታሪክ ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ እናስተዳድረዋለን ከሚሉት ሀገር አንድን ግዛት ገንጥለው ራሳቸው ዕውቅና ከመስጠትና መተዳደሪያ የሚሆናትን የጎጆ መውጫ በጀት ከመመደብ ባለፈ በአፋጣኝ ዕውቅና እንዲሰጥላቸው ጠይቀዋል፡፡ በዚህም እነኚህ ኢትዮጵያን የያዙ የወያኔ ሰዎች ቅኝ ገዢዎች እንጂ የሀገሪቱ እውነተኛ ዜጎች አለመሆናቸውን በገሃድ አሳይተዋል፡፡ ኢትዮጵያን በዜግነት ሣይሆን ለጥቅም የያዘ አካል ደግሞ የጥፋት እንጂ የልማት ተልእኮ ሊኖረው አይችልምና እስካሁን ያደረጉት ሁሉ ከዚህ መሠረታዊ ጭብጥ የተለዬ አይደለም፡፡ የሚታዩት አንዳንድ የልማት ውጥኖችና የመሠረ ልማት ዝርጋታዎችም ቢሆኑ የዕርዳታና ብድር ማወራረጃና የድጎማ ባጀትን ማስቀጠያ እንጂ እውነተኛና ሁሉን አቀፍ እንዳልሆኑ የታወቀ ነው፡፡ በዚያ ላይ ለ23 ዓመታት ሥልጣን ላይ ለነበረ አካል እነዚህ በጎ ጅምሮች የእንፉቅቅ ያህል እንጂ አታሞ ሊደለቅላቸው የሚገቡ አይደሉም፡፡ በነዚህ ዓመታት ውስጥ በሙስና በሮች በባለሥልጣናት የተመዘበረው፣ ለመከላከያና ለደኅንነት የወጣው፣ ወያኔንና ቁንጮ ባለሥልጣናቱን ለመጠበቅ የተከሰከሰው፣ አለዕቅድ በየቦታው የባከነውና በወያኔ የንግድ ድርጅቶች የተመዘበረው የሀገር ሀብት በአንድነት ተደምሮ ሥራ ላይ ቢውል ይሄኔ ሀገራችን የት ልትደርስ እንደምትችል ስናስበው ትርፋችን ጸጸት ብቻ ነው፡፡

የከፋ ዘረኝነትና አፓርታይድ የሚያካሂዱ ናቸው፡፡ የነጭ በጥቁር ላይ አፓርይድ ከደቡብ አፍሪካ ሲባረር በቀጥታ የመጣው ወደኢትዮጵያ ነው፡፡ እዚህም መጥቶ ጥቁር በጥቁር ላይ፣ ወንድም በወንድም ላይ – ትግሬ በአማራና መሰል ምዝብር ሕዝብ ላይ የተጫነ በዓይነቱ አዲስ የሆነ አፓርታይድ በታሪክ ሊመዘገብ ችሏል፡፡ ይህ በኅቡዓን የዓለም ገዢ ኃይላት አማካይነት እየተጃገነና ሁለንተናዊ ድጋፍ እየተሰጠው ሥልጣን ላይ የወጣ የኅቡዓን ኃይላት የኢትዮጵያ ክንፍ  (representative in Ethiopia of the secret lodges such as the Skull and Bones or the Order of Death) እንደነሱው ሁሉ ብዙኃንን በኃይል እየደቆሰ ወረደ መቃብራቸውን የሚያፋጥንና በምትኩም የጥቂቶችን የተንደላቀቀ ሕይወት የሚያረጋግጥ መሠሪ ቡድን ነው፡፡ ዋና ተልእኮው ብሔራዊ ስሜትን ማጥፋትና ሞራለቢስነትን ማስፋፋት በመጨረሻም የሉሲፈርን የጨለማ መንግሥት በምድር ላይ በግልጥ ማወጅ በመሆኑ ይህ ቡድን በሃይማኖቷና በባህሏ የታወቀችን አንዲት ታሪካዊት ሀገር በማጥፋቱ ረገድ በሙሉ ፈቃደኝነት በመተባበሩ እስካሁን ከየትኛውም ተፅዕኖ አሳዳሪ የውጭ መንግሥት አንዳችም ግልምጫ አልደረሰበትም፡፡ የወያኔ አፓርታዳዊ ሥራ ከደቡብ አፍሪካም እጅግ የከፋ ሆኖ ሳለ አንድም የውጭ አካል ሃይ ያለው የለም፤ ይህም የሆነበት ምክንያት በማንነት ጥያቄ ቀድሞውን ይንገላወድ የነበረው ይህ የወያኔ ቡድንና አመራሩ ምድራዊ የመብልና መጠጥ ፍላጎቶቹ እስከተሟሉለት ድረስ ለሰብኣዊና ኅሊናዊ ጤናማ ዕሤቶች ደንታቢስ በመሆኑና ለታሪካዊ የሰው ልጆች ጠላቶች ምቹ ሆኖ በመገኘቱ ብቻ ነው፡፡ ለነሱ ባይመች ኖሮ እስካሁን ስንቴ ተቀያይሮ ነበር፡፡ ለማንኛውም ወያኔ የአፓርታይድ ታሪክ አስቀጣይ የዘመናችን ባንዳ ነው፡፡ የአመራሮቹ ጥንተ ታሪክ ሲፈተሸም ሀገር ክህደትንና ባንዳነትን በደም ከአያት ቅድመ አያቻቸው የወረሱት ስለመሆናቸው ብዙ ማስረጃዎች አሉ፡፡

በትግሬዎችና በሌሎች ዜጎች ቁርጥ ያለና ለማንም ቁልጭ ብሎ የሚታይ የዜግነት ልዩነት አለ (ትግሬዎች ሲባል እንደ አጠቃላይ እንጂ በዝርዝር አተያይ የሚስተዋሉ ፈርጣዊ ቀለማትን እንደማይጨምር ማስገንዘብ እፈልጋለሁ፡፡) በመሠረቱ የዚህ ልዩነት መኖር ለኅቡዓን ድርጅቶች ዓላማዎችና ዒላማዎች ስኬት ወሳኝ ነው፡፡ በሀገሮች ውስጥ ሰላምና ፍቅር ካለ ሰይጣናዊ መንግሥትን ለመመሥረት አይቻልምና ያ ዓይነቱ ሰላማዊ መደላድል በኢትዮጵያ ብቻ ሣይሆን በተቀረው ዓለምም ሁሉ መጥፋት ይኖርበታል፡፡ ያን ለማጥፋት ደግሞ ለሀገርና ለሕዝብ የሚጠቅም መንግሥትና የመንግሥት አመራር ሳይሆን ሕዝብና ሀገር የሚጠላው ክፉ መንግሥት መተከል አለበት፡፡ የሌሎች ሀገሮችን ተሞክሮ ስናይ ሕዝብ የወደደው መሪ በመፈንቅለ መንግሥት ሲወገድና በቅጥር ነፍሰ ገዳዮች አረር አናቱ ሲበረቆስ በምትኩም ሆዳምና የሚጫነውን የምዕራብ ግሳንግስ ሁላ አለአንዳች ቅዋሜ የሚሸከም ማይም አጋሰስ በልዩ ዘዴ – የዴሞክራሲን ጭምብል በመጠቀም ጭምር – ሥልጣን ላይ ሲወጣ ነው፡፡ በኢትዮጵያ እያየነው ያለነውም ይህንኑ ነው፡፡ ትግሬው ተጠቃሚ ሆኖ ወይም ቢያንስ መስሎ የምናየው በመሠረተ ሃሳቡ ለትግሬው ታስቦ ሣይሆን የእርስ በርስ መናከስንና ጠብንና ዕልቂትን ለማነሳሳት በዚያውም የዚያን የዲያብሎስ የሰው ደም ግብር ለማቅረብ ተፈልጎ ነው፡፡ እናስ? እኛስ በመርበባቸው አልገባንም? ከመነሻው አሣፍረን ልንመልሳቸው ሲገባን የመጣብን መርገምት በረከት መስሎን አንዳችን በአንዳችን ላይ አለቅጥ ስንፏልል ይሄውና የእግዚአብሔር ቅጣት በኛና በልጆቻችን ላይ ሊወርድ የቀረው ጊዜ እጅግ አጭር ሆነ፡፡ በወያኔ የዱባ ጥጋብ የተዘናጋው ትግሬ፣ በተለይ በአማራው ላይ በመነሳቱ ምን ጥቅም አተረፈ? ሁላችንም ረጋ ብለን እናስበው፡፡ በአንዱ ሞትና ስደት ሌላው መጥገቡና ሰማይ ጠቀስ ሀብትና ንብረት ማከማቸቱ እየቆዬ ለኅሊና ፀፀት የሚዳርገው ከሆነ፣ እየቆዬ የ‹ወይኔ›ን እግር እሳት በመላ ሰውነቱ የሚለቅበት ከሆነ፣ እየቆዬ ጥጋቡ ወደርሀብ የሚነዳው ከሆነ ከፀሐይ በታች ምን አዲስ ነገር አመጣለት ሊባል ይሆን?  የቀንን ጎደሎ ያልተረዳ ትግሬ ሥልጣን ላይ ያለውን ገዢ ኃይል ተጠቅሞ የአማራውን ሕዝብ ሀብትና ንብረት በመቀማቱ እስከመቼ እንደተደሰተ ይኖራል? አዙሮ ማየት ማንን ገደለ? ሆድንና ስሜትን ሳይሆን አእምሮንና ኅሊናን መጠቀም ማንን ጎዳ? ጊዜ መልሱን የሚሰጣቸው ብዙ ጥያቄዎችን መጠየቅ ይቻላል፡፡…

ወያኔ ኤድስ የያዛቸውን ዜጎች ከትግራይ አንድ ባንድ እየለቀመ አማራውን እንዲፈጁለት ወደተለያዩ የአማራው አካባቢዎች ተገቢውን ሥልጠናና ንቃት በመስጠት ታማሚ ትግራውያንን ታመውም እንኳን በተጋዳላይነት አሰልፎ ሟቾችን በጤናማ ዜጎች ላይ እንዲዘምቱ ለልዩ ተልእኮ ያሰማራቸው ነበር፡፡ ትግራይ ውስጥ ሳይቀር ሀገራቸውንና ኢትዮጵያዊ ባንዲራቸውን የሚወዱ ትላልቅና ታላላቅ የትግራይ ተወላጆችን በወባ መቆጣጠሪያ ክኒን መልክ በሚዘጋጁ መርዞች እየበከለ ይጨርሳቸው እንደነበርም ይታወቃል – ይህ ዓይነቱ ዜጎችን በልዩ ልዩ ሥልትና ዘዴ እየገደሉ በሚሰጠው ስሜት መደሰትና መዝናናት መለስን በመሳሰሉ ሴተኒስቶችና የኅቡዓን ማኅበረሰብ ቀንደኛ አባላት መካከል ጌታቸውን ሊቀ ሣጥናኤልን በደስታ የሚያስፈነድቅ እጅግ ተፈላጊ ተግባር ነው፤ ያሾማል ያሸልማልም፡፡ (It is one among the satanic ritual abuses /SRA/.)

ወያኔ ‹ዓሣን ለማጥፋት ባህሩን ማድረቅ› በሚል መፈክሩ በዋና ጠላትነት የፈረጃቸውንና ባገኘው መሣሪያና ሥልት ሁሉ ከምድረ ገጽ ለማጥፋት የሚሌኒየሙን ትልቅ ዘመቻውን የከፈተባቸውን የአማራ ልሂቃን ለወደፊቱ ከመባቀያቸው ድራሻቸውን ለማጥፋት በአማራው ብዙ አካባቢዎች አምካኝ መድሓኒቶችን(መርዞችን) ማደሉ የሚታወቅ ነው፤ ሰሞኑንም በልዩ ልዩ ‹ነጻ ሚዲያዎች› በይፋ ተገልጾኣል (ይቅርታ – ‹ነጻ ሚዲያ› አለ ብዬ ስለማላምን ነው – አስቸጋሪ የክርክር ነጥብ ይመስለኛል፤ ‹ነጻ› የሞተ ብቻ ነው – የምትደግፈው ከሌለ የምትቃወመውም የለም – እንደ አካሄድ!)፡፡ በዚህም ሳቢያ በአሁኑ ወቅት በብዙ የአማርኛ ተናጋሪ አካባቢዎች ባልተለመደ ሁኔታ ትምህርት ቤቶች ተመዝጋቢ ሕጻናትን እያጡ ሊዘጉ መቃረባቸውን፣ ብዙ መንደሮች ውስጥ ለአምሮትም እንኳን የሚሆን አንድም እምቡር እምቡር የሚል ሕጻን አለመገኘቱን፣ አዲስ ተጋቢዎችና ነባር ወላዶች በልጅ ስጠን ተማጥኖ ጠበሎችንና አውሊያ ቤቶችን ሙጥናን ማለታቸውን፣ ወዘተ. በቅርቡ የወጣ ማጋለጫ መግለጫ አስታውቋል፡፡ይህን ዓይነት ሥራ ከሰይጣን በስተቀር ሌላ የሰው ልጅ ሊሠራው እንደማይችል መረዳት ይገባል – ወያኔዎች ሰይጣን ያደረባቸውና እንዲያውም ከራሱ ከሰይጣን በላይ ለጌታቸው መንግሥት አደግድገው የቆሙ ቅን ታዛዦች ናቸው፤ ሰው ምን አረመኔ ቢሆን ይህን ወንጀል አይሠራም – በጭራሽ፡፡ ለነገሩ በጃንጥላ እየወረደ የሚገኝን የጦር ምርኮ አየር ላይ በጥይት ከሚቀላ የአጋንንት ውላጅ ወያኔ መልካም ነገር አይጠበቅምና በአማራውም ሆነ በሌላው ላይ የሠራውና የሚሠራው ይህን መሰሉ ግፍና በደል ሁሉ ሊሠራው ከሚችለው በታች እንጂ በላይ ሊሆን አይችልም፡፡ ምክንያቱም ተፈጥሮው ጥፋትና ከጥፋትም ነውና፡፡ ወያኔ የተሠራበት ጭቃ ወደ አፈርነት የተለወጠው ሔዋንን ያሣታት እባብ ቅሪተ ከይሲ አፈር ነው፡፡

ኢትዮጵያውያን እኩል ዜግነት እንዳይሰማቸው አንዱን በላተኛ ሌላውን የበይ ተመልካች አድርጓል፡፡ ሥልጣንና ሀብት በአብዛኛው በትግሬዎች እጅ እንዲገኝ በሕግ ሽፋንና በጉልበት የሚችለውን ሁሉ አድርጓል፡፡ ኢትዮጵያ የትግሬ ብቸኛ ሀብት መስላ እስክትታይ ድረስ ወያኔ አንዳችም ይሉኝታ ሳይኖረው ሁሉንም ምርጥ ምርጥ ነገር -አንድም ሣይቀር – ለትግራይና ለትግራውያን እንዲሆን ያደረገ ለትግሬዎች ብቻ ሣይሆን የሰው ልጆች ዘር አጠቃላይ ማፈሪያ ነገር ነው፡፡ ይህ እውነት፣ እውነት እንጂ የፈጠራ አይደለም፡፡ የሚጠራጠር ሰው ካለ መዛግብትን ያገላብጥ ፤ ወደ ኢትዮጵያ መጥቶም እኛን የቁም ምሥክሮችን ያነጋግር – የሠፊው ቃሊቲ እሥረኞች ነን ማለትም ይቻላል፡፡ በኢሳት አማካይነት የሚሠጡ እውነተኛ ምሥክርነቶችንም በአድራሻቸው ገብቶ ያንብብ ወይም ያድምጥ፡፡ ለምሳሌ ሰሞኑን ከሰማሁትና በፊትም ከማወቀው ለመጥቀስ ያህል አየር ኃይላችንን እንዴት እንዳጠፉትና ለሥልጠና የሚልኳቸው ደረጃቸውን ያልጠበቁ ዜጎች ሁሉም ከትግራይ እንደተመለመሉ የሚጠቁመውን በቦታው የነበረ የባለሙያ ገለጻ ማየት ይቻላል፡፡ ይህ የአሁኑ ትውልድ በዚህ አስገራሚ የታሪክ አንጓ ላይ የመገኘታንን አጋጣሚ ስታዘብ ፈጣሪ ምን ያህል ሊቀጣን እንደወደደ ትውስ ይለኝና በአግራሞት እወሰዳለሁ፡፡ እንደኛና የኛን ያህል የተቀጣ ሕዝብ ስለመኖሩም እጠራጠራለሁ፡፡ በጥይትም ሆነ በቦምብ አንዴ መሞት ፀጋ ነው፤ የኛ ግን ከወያኔ የሥልጣን ይዞታ የመጀመሪያ ዕለት አንስቶ በኅሊና በየሰከንዱና በየደቂቃው እየሞትን እንገኛለን፡፡ እውነቴን ነው የምለው – ስለወያኔ የአድልዖ ሥራ ባስታወስኩ ቁጥር ኢትዮጵያዊነቴን ብቻ ሣይሆን ሰው ሆኜ መፈጠሬን ጭምር እጠላለሁ፡፡ ይታይህ – ትግሬ በመሆንህ ብቻ የኢትዮጵያ ጓዳ ጎድጓዳ ለአንተ እንደልብህ የምትፏልልበት የራስህ ንብረት ሆኖ ለአንተ ለምሥኪኑ አማራ ወይም ሽናሻ ግን በዐይንህም እንዳታየው እንደውሻ ችው የምትባልበትና በአካባቢው ዝር እንዳትል በዱላ እየተቀለጠምክ የምትባረርበትን ሁኔታ ስትታዘብ በሰዎች ግብዝነትና አለማፈር ታፍራለህ – ደግ ሰው ከሆንክም የነዚህን ዓይነት ቂላቂል ሰዎች መጨረሻ ፈጣሪ ቀለል እንዲያደርግላቸው ልትጸልይላቸው ትችላለህ፡፡ የትም ስትገባ ፈላጭ ቆራጩ ትግሬ የመሆኑ ምሥጢር አልገባህ ይልናም ክፉኛ ልትተክዝ ትችላለህ፡፡ ይህ ነገር መቅሰፍት እንጂ ምን ሊሆን ይችላል? መቀሰፍት ደግሞ መቅሰፍትን ይጎትታል! እንደ እውነቱ ያለንበት ሁኔታ ሲታይ የህልምና የቅዠት እንጂ የእውን አይመስልም፡፡ ፈጣሪ ሰውን በመሥራቱ መጸጸት ካለበት ጊዜው አሁንና አሁን ብቻ ነው – የወያኔን ከዲያሎብስ የበለጠ ክፋትና ክፋተኝነት ሲያይ፡፡ እንዴ! እንኳንስ በጽንሰትህ በሞትህም እኮ አይለቁህም!

ትምህርትን በሚመለከት ከትግራይ ውጪ ሁሉም የሞተ ያህል ነው፡፡ ትውልድን ለመግደል ሲታሰብ ቀድሞ ዒላማ ውስጥ የሚገባው ትምህርት ነው፡፡ የትምህርትን ጥራት ከገደልክ ሀገርንም ትውልድንም በአንድ ጥይት ደብድበህ ትገድላለህ፡፡ ወያኔም ደርግ ያቆሰለውን ትምህርት ጨርሰው ገድለው ቀብረውታል፡፡ ‹ሀሁ›ንና ‹አቡጊዳ›ን በቅጡ የማይለዩ የኮሌጅ ምሩቃን አገሩን አጥለቅልቀውት ስታይ የትና መቼ በማን የተማረ የሰው ኃይል ሀገሪቱን ሊረከብ እንደሚችል በማሰብ ልትጨነቅ ትችላለህ፡፡ መሬቲቱ ምሁራንን ሳይሆን …

በሀገሪቱ ቅጥ ያጣ ድህነት ተስፋፍቷል፡፡ ጥቂቱ በጥጋብ ቁንጣን ሲጨነቅ ብዙኃኑ ይልሰውንና ይቀምሰውን አጥቷል፡፡ የሀብት ክፍፍሉ ሰማይና ምድርን ያህል የተራራቀ ነው፡፡ ኢፍትሃዊነት ነግሷል፡፡ ሠራተኞች ተገቢ ክፍያ አያገኙም፡፡ የወያኔው ሥርዓት የሚደግፈው ሀብታሞችን እንጂ ተቀጣሪ ድሆችን አይደለም፡፡ በዚህና በሌሎችም ምክንያቶች ሳቢያ፤-

ልመናና ቧጋችነት ከምን ጊዜውም በበለጠ በሀገሪቱ የባህል ያህል ተንሰራፍቷል፤ ዛሬ መለመን አያሳፍርም፡፡ የማይለምን ሰው በነውረኝነት እስኪፈረጅ ድረስ ከትልቅ እስከ ትንሽ አብዛኛው ሰው ለማኝ ሆኗል፡፡ ልመናና በረንዳ አዳሪነት በጣም ከፍተኛ ደረጃ ላይ ደርሰዋል፡፡ ሴተኛ አዳሪነትም የዚያኑ ያህል ነው – የወሲብ ገበያው ከዐዋቂ እስከ ሕጻን እጅግ ደርቷል፡፡ ሽርሙጥናው በተለመደው የተቃራኒ ፆታ መካከል ብቻም እንዳይመስልህ – በተመሳሳይ ፆታም ብሷል፡፡ ብዙ ነገሮች ከመስመር ወጥተዋል – የሶዶምና ገሞራንም መዐት እየጋበዙ ይመስላል፡፡ ለዚህ ሁሉ የሞራል ዝቅጠትና የሃይማኖት መላላት ዋና ተጠያቂው የነእንትና እንደራሴ የሆነው ወያኔ መሆኑን ታዲያ አትርሣ፤ እግዚኦ በል – እግዚኦ እንበል፡፡ ቢሆንም …ቢሆንም… አይዞን ጊዜው ቀርቧል፤ ዘመኑ አልቋል፡፡ የምዕራፍ ሁለት የጅማሮው ብሥራት ገመገሙ እየታዬ ነውና አንተ ብቻ እንዳትሰናከል በርታ፤ አምላክህ እንዲረዳህም ለምነው፡፡ ከርሱ ብቻ ግን አትጠብቅ፤ ለነጻነትህ አንተም የድርሻህን ተወጣ፡፡

በሀገሪቱ ፍትሃዊ አስተዳደር ጨርሶውን የለም፡፡ ጉልበተኝነትና ዘረኝነት ትልቁን ሚና ስለሚጫወቱ ሕግ አለ ብለህ የትም ብትሄድ ዋጋ የለህም፡፡ የፈጣሪ ጥበቃ እንጂ አንድም ቦታ ፍትህና ርትዕ የለችም፡፡ ብትከስ ወይ ብትከሰስ ዋቢህ ገንዘብህ ወይም ጎሣዊ ማንነትህ ብቻ ናቸው፡፡ በጠራራ ፀሐይ አንዱ ትግሬ ወያኔ ንብረትህን ቢዘርፍህ ዕንባህን ወደላይ ፈንጠቅ ከማድረግና የላይኛውን ፍርድ በትግስት ከመጠበቅ ውጪ የሚረዳህ ፍርድ ቤትም ሆነ የሕግ ቦታ የለም – አንዲት ቀጭን የሥልክ ትዕዛዝ ሰበር ሰሚ ተብዬውን ‹ግዙፍ› ፍርድ ቤት አፉን ልታዘጋ ትችላለች – ያቺ ቀጭን ትዕዛዝ ደግሞ ከየት እንደምትመጣ አታውቃትም፤ ‹ጠ/ሚ› ኃ. ደሳለኝን ከመሰሉ ኮንዶሞች እንደማትሆን ግን መረዳት አለብህ – ፍትህን በማዛባት ረገድ ይተባበሩና በታዛቢነት ያገለግሉ እንደሆነ እንጂ እነደመቀ በወሳኝነት ሚና አይታሙም፤ እነሱ ምን ቤት ናቸውና፡፡ የንብረትህ ብቻ ሣይሆን የነፍስህም ፈጣሪ ወያኔዎችና በወያኔነት ያበዱ ትግሬዎች  ናቸው፡፡ (ጤነኞች ትግሬዎች የዛሬን ታገሡኝ ግዴላችሁም – የሆድ የሆዴን ልዘርግፈውና ልገላገል፡፡ ደግሞም ጥሩ ዕቃ ማስታወቂያ እንዲነገርለት አያስፈልገውምና ጥሩዎች ትግሬዎች ብዙም እንደማትከፉብኝ ብገምት ደስ ይለኛል፤ እነዲያቆን እገሌ ግን ቢንጣጡ ግዴለኝም – ለሁለት ዓለም  የሌሊት ወፍ መሰል ዜጎች ተጨንቄ አላውቅም፡፡ ከወያኔያዊ እድፍ የጸዳን ነን ብላችሁ የምታምኑ ጥሩዎች ትግሬዎች በምናገረው ብሶት ስሜታችሁ እንደሚጎፈንን ይገባኛል – ግን እንዳትፈርዱብኝ፡፡ በኔ ቦታ ሆናችሁ እዚህም ሆነ እዚያ የሚነገሩ እውነቶችን ለመቃኘት ሞክሩ፡፡ ስትቃኙ በጭፍን አይሁን፤ ስህተት እንኳን ብናገር ለስህተቴ መነሻው ማን እንደሆነ ተገንዘቡልኝ፡፡ ደግሞም የምለው ሁሉ የሚገናኘው ከወያኔና ጀሌዎቹ ጋር እንጂ ከችግሩ ተቋዳሽ አብዛኛው የትግራይ ሕዝብ ጋር አይደለም፡፡ እንደዚያ ሊሆንም አይችልም፡፡ ከአድማስ ማዶ ሀገር ያለ እንኳን የማይመስለው ንጹሕ ዜጋ በነዚህ ስድ አደግ ወገኖቹ ሊወቀስ እንደማይገባው እኔ ቀርቼ ጡት ያልጣለ ሕጻንም ያውቃል፡፡ ‹ከአጋም የተጠጋ ቁልቋል ሲያለቅስ ይኖራል› እንዲሉ ሆኖብን ባልገው በሚያባልጉ ወገኖች ስሜታችን እየተነካ ጥሬ እውነቱን እንዳለ ስንናገር ለትዝብት እንዳረጋለን፡፡ ለማንኛውም በነዚህ ጉግማንጉግ ወንድሞቻችን መጥፎ ድርጊት ምክንያት ስማችንን አጠፋህ ለምትሉኝ ወገኖቼ በማቄን ጨርቄን ምንም ሰበብ ሳልደረድር ልባዊ ይቅርታችሁን እጠይቃለሁ፤ የመካካስ ዘመን ሲብት(ም) በፍቅር እቀጣለሁ፡፡)

ሙስና እግር አውጥቶ ታየዋለህ፡፡ በእጅህ ካልሆነ በእግርህ ሄደህ የሚፈጸምልህ ጉዳይ ከስንት አንድ ነው፡፡ ይህን አሠራር ሆን ብሎ የሚያበረታታውም ወያኔ ነው፡፡ ከሞላ ጎደል ሁሉም ባለሥልጣን ሙስና ውስጥ የተዘፈቀ ነው፡፡

የኑሮ ውድነቱ ከጣርያ በላይ ነው፡፡ ዛሬ እህል ቀምሶ የሚያድረው ዜጋ ቁጥር ከምን ጊዜውም በላይ እጅግ ጥቂት ነው፡፡ ኢትዮጵያውያን ችግርን በመቻል ስለሚታወቁ ሲስቁና ሲጫወቱ የደላቸው ይመስላሉ እንጂ ሁሉም በየቤቱ አፍኖ የያዘው ችግር ቢፈነዳ ሀገሪቱ የችግር ኮረጆ እንደመሆኗ መዘዙ ወይም ዳፋው በቀላሉ የሚገደብ አይደለም፡፡ በግርድፍ ግምት ከ40 ዓመታት በፊት የነበረው አንድ ብር የዛሬውን ቀልበቢስ መቶ ብር አሳምሮ ይበልጠዋል፡፡ የዛሬው ግርማ ሞገሱ የተገፈፈ መቶ ብር መልክ ብቻ እንጂ ሙያ የለውም፡፡ እንደሁለተኛው የዓለም ጦርነት ጀርመን ልንሆን የቀረን ጥቂት ጊዜ ነው – እስካሁን ወደዚያ ያልደረስነውም በፈጣሪ ጥበቃና በእርሻ ምርቶች ባለቤትነታችን ነው፡፡ አብዛናውን የእህል ምርት ከውጪ የምናስገባ ብንሆን ኖሮ እስካሁን የለንም፡፡ በዚህ እግዜሩ ይመስገን፡፡

ወያኔ የኢትዮጵያን ሉዓላዊነት የሸጠ የወሮበሎች ቡድን ነው፡፡ የሕዝብን መብት አለማክበርና ዘወትር ዜጎችን መግደል የአምባገነኖች ባሕርይ ነው ብንል ወያኔ ግን ከመሰል አምባገነኖች በተለዬ ሁኔታ የሀገርን ግዛትና ለም መሬቶች ለውጪ ሀገሮችና ለውጪ ኢንቬስተሮች ባገኘው ዋጋ እየቸበቸበ በሚገኘው ገንዘብ በግሉ የሚከብር የከተማ ሽፍቶች ጥርቅም ነው፡፡ እነዚህ ወሮበሎች አገዛዙን የሚቀማቸው ጀግና አጥተው እንጂ ሀገሪቱን በኳስ አበደች ትርምስ ውስጥ ከትተው ቀደም ካለ ጊዜ ጀምረው ወዳዘጋጁት ሰሜናዊ የትግራይ ትግሪኝ ግዛታቸው  ለማምራት ያቆበቆቡ ይመስላሉ፡፡ ሁሉንም የመከላከያ ተቋም ወደ ትግራይ እንዳዞሩ የሚነገረውም ከዚህ መሠረታዊ የሽፍቶቹ አቋም ጋር በተገናኘ መሆን አለበት፡፡ በ23 ዓመታት ውስጥ ቅንጣትም ኢትዮጵያዊነት ስሜት ሊያድርባቸው ያልቻሉት እነዚህ በአስተሳሰብና በድርጊት ባዕዳን የሆኑ ገዢዎቻችን ነገና ነገ ወዲያ ምን አጥምደውብን እንደሚሄዱ ማወቅ አንችልም፡፡ ቢሆንም መታመን በፈጣሪ ነውና እርሱ ራሱ ያከሽፈዋል ብለን የምናምን ምሥኪን ዜጎች እነሱ ለራት ሲያስቡን አንድዬ ለምሣ ያደርጋቸው ዘንድ በርትተን እንጸልይ፡፡

ሃይማኖታችንን በየዘርፉ ለማጥፋት በከፍተኛ ደረጃ ተንቀሳቅሰዋል፡፡ በዚህም ብዙ ተሳክቶላቸዋል፡፡ ኦርቶዶክሱን ከሞላ ጎደል አጥፍተዋል፡፡ የመጥፋቱ ምልክት ሁሉንም አመራር በሃሳዊ መሲህ የትግሬዎች ካህናትና ሰሜነኞች የቤተ ክርስቲያን ‹አባቶች› ቁጥጥር ሥር ማስገባታቸው አይደለም – ያ በራሱና ብቻውን ጥፋት አይደለም( በበኩሌና በመሠረቱ ሁሉንም የዓለማዊና ሃይማኖታዊ ሥልጣን ትግሬ ቢይዘው አንዳችም ቅሬታ የለኝም፤ ችግሬ ዐይኑን እያጉረጠረጠ የሚገኘው ዜጎችን እየቆረጣጠመ፣ ሀገርን እያወደመ ያለው የአድልዖና የማግለል ሥራቸው ነው – የዚህ ችግር መሠረትም ማይምነትና የጥቂትነት ባሕርይ የሚያሳድረው የበታችነት ስሜት፣ ያንንም ስሜት በቅጡ ካለማስተዳደር የሚመጣ ስግብግብነትና ራስ ወዳድነት፣ እንደዚሁም ሌሎችን ያለማመንና ‹ይችን ዕድል ካጣሁ ዳግመኛ ወደዚች ቦታ አያስደርሱኝም› ከሚል ፍርሀት የሚመነጭ ‹የሞኝ ሙርጥ ካለአንድ ቀን አይበልጥ› ዓይነት አስቀያሚ አጋጣሚ ነው – እንጂ ትግሬዎች በተፈጥሯቸው መጥፎና ይህን ያህል ጨካኝ ሆነው አይደለም – ነገሩ የሆድ ነገር ሆድ መቁረጡ ነው የማይዘሉት ፈፋ ሆኖ ብዙዎቹን ያስቸገራቸው፡፡  ይህ ዓይነቱ ማኅበረሰብኣዊ በሽታ በወደፊቱ የአብሮነት ሕይወት የሚጥለውን አሉታዊ አንድምታ ከአሁኑ ጀምሮ መርሳትን መለማመድ ጊዜን ይቆጥብልናልና በ‹ልጅሽን አንሺ ምጡን እርሺ› ይትበሃላችን ወይዘሪት ነጻነትን ለሁላችንን በሚጠቅም ጉጉት እንጠብቃት ብል በ‹መብላቷን ሳታውቅ እጇን ታጠበች› ብሂል የምጎሸም ችኩል የምሆን አይመስለኝም – ጊዜው በጣም የቀረበ ይመስለኛልና – እኔ አላውቅም ግን እንደዚያ ይመስለኛል፡፡) ዋና ምልክቱ ታዲያን የሚሠራው ሥራ ሁሉ የመርገምት መሆኑና ያም መርገምት መቅሰፍትን የሚጠራ የኃጢኣት ፍሬ መሆኑ ነው፡፡ በየአድባራቱ ብናይ የሚሠራው ሥራ ሁሉ ክርስቲያናዊ ሣይሆን የማስመሰል ነው፡፡ በማስመሰል ሥራ ደግሞ ትክክለኛ ሃይማኖት አትቆምም፡፡ የማያዛልቅ ጸሎት ለመብረቅ እንደሚዳርግ መነገሩም ለዚህ ነው፡፡ እናም ቤተ ክርስቲያንም ልክ እንደ ቤተ መንግሥታችን ሁሉ የጽዳት ዘመቻው እኩል ተቋዳሽ ናትና ‹ቀበጥ አማት ሲሦ ብትር አላት› እንዲሉ አሣሯን ስትበላ የምናይበት አጋጣሚ ከፊት ለፊቷ ሳይደቀን አልቀረም፡፡ ቤቴ ብለው የተጠጉ ልጆ‹ቿ›ን ለነቀያፋና ለነጲላጦስ እንደይሁዳ በመሳም አሳልፋ የሰጠችና የምትሰጥም ቤተ ክርስቲያን ብትቀጣ በበኩሌ ዐይኔ ዕንባ የሚያቀርር አይመስለኝም – ቀላሉን ያድርግላት ብሎ መጸለይ ነው፡፡ በወደዱት መቁረብ ዛሬ አልተጀመረም፡፡ ከቻለች ይልቁንስ ከነዚህ በአጋንንት መንፈስ ከተሞሉ ወያኔዎች በቶሎ ትለይ  – ይህ ዓለምን ከዳር እዳር እየናጠ ያለ መንፈስ በራሷ ውስጥ እንደሌለ ካሰበች መፍትሄው ይሄው ብቻ ነው – ወደቀደመው የሃይማኖት ቀኖና መመለስና ቤትን በራስ ጊዜ ማጽዳት፡፡ አለበለዚያ የርሷ እንደሚቀድም መተንበይ አይከብድም፤ ምክንያቱም አባት ከልጅ ቀድሞ ሊያልፍ ይጠበቃልና፡፡

ወያኔዎች ይሉኝታ የሚባል ሀበሻዊ ንጥረ ነገር ከነአካቴው ኖሯቸው የሚያውቅ ከሆነ አላውቅም፡፡ በአሁኑ ሁኔታቸው ግን በፍጹም እንደሌላቸው ግልጽ ነው፡፡ ይሄ ይስማዕከ ወርቁ የሚባል ትልቅ ተስፋ ያለው ወጣት ደፋር ደራሲ በነዚያ የዴርቶጋዳ የዋሻ ውስጥ ምናባዊ ሣይንቲስቶቹ አማካይነት ከወደፊት ልቦለዶቹ በአንደኛው ይህን በወያኔዎች ሰውነት ውስጥ ተፈልጎ ለናሙናነት ያህል እንኳን ሊገኝ ያልቻለ ይሉኝታና ሀፍረት በላቦራቷር ካላሠራላቸው በስተቀር አሁንስ ክፉኛ ያሳዝናሉ፡፡ ወያኔ ትግሬዎች ሱቅ ውስጥ እንደገባ ሕጻን የኢትዮጵያ ሕዝብ የጋራ ሀብትና ንብረት የሆነን ሁሉ ለብቻቸው እየተሻሙ ለግላቸው እያዋሉት ስለሆነ ሌላው ዜጋ ለስደትና ለጦም አዳሪነት ተጋልጧል፡፡ በዚህም ምክንያት፡-

ከጥቅም ተጋሪ ወያኔ በስተቀር  ሁሉም ዜጋ ለስደት ተዘጋጅቷል፡፡ በሀገር ውስጥ የበይ ተመልካች ሆኖ በችግርና በችጋር ከሚጠበስ በሰው ሀገር ሄጄ ገረድና አሽከር ሆኜ ሕይወቴን ላትርፍ ብሎ በየአቅጣጫው ወደውጪ የሚተመው ሕዝብ ብዛት የትዬለሌ ነው፡፡ ያንንም ዕድል ሳያገኝ የባሕር ዓሣ ነባሪና ሻርክ፣ የበረሃ አንበሣና ጅብ ሲሳይ ሆኖ የሚቀረው ከርታታ ወገን ከቁጥር በላይ ነው፡፡ ለዚህ የወገን ስደትና እንክርት ተጠያቂው ወያኔ ብቻ ነው፡፡ ያለን የተፈጥሮ ሀብት ለሁላችንም መብቃት ሲችል በተንሸዋረረ የዘር ፖለቲካ የሚመራው ወያኔ ለዚህ ዓይነቱ ችግር አጋልጦናልና የሚመጣውን ቀውስ የሚያወራርደው ይበልጡን ወያኔ ነው፡፡

ወያኔዎች በማንአለብኝነት የምርጫ ድምጽ አጭበርባሪዎች ናቸው፡፡ ለታይታ ብለው በሞከሩት የ97 ምርጫ ብዙ ሕዝብ ጨርሰዋል፡፡ አሥረዋል፤ አሰቃይተዋልም፡፡ ሀገሪቱ በሞላ እሥር ቤት እስክትመስል ድረስ ከዳር እዳር ዜጎችን በጅምላ በማፈስ ልዩ የምርጫ ነክ ትርዒት ለዓለም አሳይተዋል፡፡ በዚያም በሀገሪቱ ላይ ከፍተኛ ሰብኣዊና ቁሣዊ ኪሣራ አስከትለዋል፡፡ ይህ ፖለቲከኞችንና የመብት ተሟጋቾችን የማሰርና በ‹የእምዬን ወደ አብዬ› ግልብጥ ክስ ዜጎችን በሽብርተኝነት ዘብጥያ የማውረድ መጥፎ ወያኔያዊ ልክፍት አሁንም በስፋት ቀጥለዋል፡፡ ወያኔዎች እንደ አራስ ውሻ ነፍርተው ለያዥ ለገራዥ በማስቸገር ሕዝብንና ሀገርን የማደፍረስ ታሪካዊ ተልእኮኣቸውን በስፋት ቀጥለዋል፡፡

ወያኔን ‹የሚያስቀስፉ› እጅግ ብዙ ነገሮችን መዘርዘር ይቻላል፡፡ ከዚህ በኋላ ያለውን ግን አንባቢ እንዲጨምርበት ተትቷል፡፡ በበኩሌ ቤት ያፈራውን ሁሉ ለነገየ አንድም ሳላስቀር የመናገር አቅሜ በፈቀደ ተናግሬያለሁ፡፡ ሌላውን አክሉበት፡፡ በቃ፡፡

 

 

Hiber Radio: ጋዜጠኛ መሳይ መኮንን ትናንት በቨርጂኒያ ስለተደረገው ሃገራዊ የውይይት መድረክ ተናገረ

$
0
0

ጋዜጠኛ ሃብታሙ አሰፋ

ጋዜጠኛ ሃብታሙ አሰፋ

የህብር ሬዲዮ ዕሁድ ነሐሴ 12 ቀን 2005 ፕሮግራም

>

ጋዜጠኛ መሳይ መኮንን ኢሳት የጠራውን በአገር ውስጥና በውጭ ያሉ አብዛኞቹን የዲሞክራሲ ሀይሎች ያሳተፈውን አገራዊ የውይይት መድረክ አስመልክቶ ከህብር ሬዲዮ ተጠይቆ ከሰጠው ማብራሪያ (ሙሉውን ያዳምጡት)

>

አቶ አስናቀ ሞላ በግብጽ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ስደተኞች ማህበር የሕዝብ ግንኙነት ሀላፊ

>

ዶ/ር አክሎግ ቢራራ በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ከህብር ሬዲዮ ጋር ካደረጉት ቃለ ምልልስ(ክፍል አንድ የተወሰደ.) ሙሉውን ያዳምጡት (ሌሎችም ቃለ መጠይቆች አሉን)

ዜናዎቻችን
- የሙስሊሙ ትግል አስተባባሪዎች የአገዛዙን

- በሼሁ ሞት የመንግስት እጅ እንዳለበት ጥርጣሬ ማጫሩን ገለጹ

- ቦሌን ከፈንጂ አደጋ አዳንነው ሲሉ የአገዛዙ የጸጥታ ሰዎች ገለጹ

- ሕዝቡ ኢቲቪ ድራማውን ጀመረ እያለ ነው

- በሳዑዲ አጎቴን ገድያለሁ ያለው ኢትዮጵያዊ በፖሊስ ቁጥጥር ስር ዋለ

- ድምጻዊ እዮብ መኮንን አረፈ

- የግብጽ የሽግግር መንግስት የሙስሊም ወንድማማቾችን በሕግ ለማገድ ማሰቡን ገለጸ

ሌሎችም ዜናዎች አሉን


በእውቀቱ ስዩም ስለ ድምፃዊዉ ኢዮብ መኮንን

$
0
0

eyobከበእውቀቱ ስዩም

ከጥቂት አመታት በፊት ባንድ የበጎ አድራጎት ትርኢት ላይ ለመሳተፍ፣ከዘፋኞች ጋር ወደ ደሴ ተጉዠ ነበር፡፡የተሣፈርንበት አውቶብስ ጉንጫቸውን በጫት አሎሎ በወጠሩ ዘፋኖች ተሞልቷል፡፡ ዘፋኞቹ ሲሻቸው ይተራረባሉ፣ ሲሻቸው ይጮሃሉ፣ይጨፍራሉ፡፡የአውቶብሳችን ሽማግሌ ሹፌር ሳይቀር፣ አልፎ አልፎ መሪውን እየለቀቀ በማጨብጨብ በ‹‹ቅወጣ›› ከዘፋኞች እንዳማያንስ በማሳየት ላይ ነበር፡፡በጫቱም፣ በጭፈራውም የሌለበት ድምጻዊ ኢዮብ መኮንን ብቻ እንደሆነ ተመለከትሁ፡፡ በርጋታ ተቀምጦ፣ ባውቶብሱ መስኮት አሻግሮ፣ የሚሮጡ የግራር ዛፎችን ይመለከታል፡፡ልዩነቱ ግልጽ ነበር፡፡
ድሮ ድሮ፣ኢዮብ መኮንን አቤሴሎም የሚዘናፈል ረጅም ጸጉር ያለው ጎልማሳ ነበር፡፡ድንገት ጸጉሩን ተሸለተ፡ከጸጉሩ ጋር የጥንት ባህርይውን አራገፈ፡፡ጭምት መንፈሳዊና በመጽሐፍ ቅዱስ ፍቅር የነደደ ምእመን ሆነ፡፡
በተገናኘን ቁጥር፣ኢዮብ ስለ ስለ እምነት እንድንወያይ ይፈልጋል፡፡ብዙ ጊዜ እምነት የሚያጠብቅ ሰው አንዳች ችግር ይኖርበታል ብየ አስብ ነበር፡፡ኢዮብ ግን እጅግ መልካም ሊባል በሚችል ሕይወቱ ይሄንን አመለካከቴን ውድቅ አድርጎብኛል፡፡
የዛሬ ሳምንት ገደማ ኢዮብ ዘፈን በመሥራት ላይ ነበር፡፡እና ላንድ ዜማው ግጥም እንደሠራለት ጋበዘኝ፡፡ከዚህ በፊት የሞርኳቸው የዘፈን ግጥሞች ስለከሸፉብኝ ግብዣውን ለመቀበል አመነታሁ፡፡ግን ደሞ ወድያው፣ በኢዮብ ድምጽ ግጥሜን ተዘፍኖልኝ ለማየት ጓጉዋሁ፡፡ውሀ ልማት አካባቢ፣ ሌክስፕላዛ ሕንጻ ሥር መኪናው ውስጥ ቁጭ ብለን ዜማዎችን ማድመጥ ጀመርን፡፡ዘፈኑ ውስጥ ያሉት ሐሳቦች አብዛኞቹ ወደ መዝሙር ያዘነብላሉ፡፡ ኢዮብ ዘፈኑን ለፈንጠዝያ ሳይሆን ለስነምግባር ግንባታ ሊጠቀምበት ፈልጓል፡፡አንድ በጣም ልብ የሚበላ የሶማሌ ዘፈን አስደመጠኝ፡፡
‹‹ሶማሊኛ ትችላለህ እንዴ?>>
‹‹አዎ፣ትግርኛም አውቃለሁ!››
‹‹የት ተማርከው?>>
‹‹አስመራ፣የወታደር ልጅ መሆኔን አትርሳ››
ከዘፈን ውጭ ምን ታደርጋለህ?
‹‹ኦን ላይን፣ ጊታር እየተማርሁ ነው፡፡ቆይ ላሳይህ››…ላፕቶፑን ለኮሰና ጥቂት አስጎበኘኝ፡፡ከዛ ከመኪናው ስወርድ የመኪናው እጀታ ስለማይሠራ ወርዶ ከውጭ ከፈተልኝ፡፡ኢዮብ ብዙ ብሮችን መቆጠር የሚችል ልጅ እንደሆነ መገመት ይቻላል፡፡ይሁን እንጂ እንኳን መኪናውን የመኪናውን እጀታ ማስቀየር አልፈለገም፡፡ምናልባት፣ዓመት በአልን ጠብቆ ልብስ የሚቀይር ብዙ ሰው ባለበት አገር ውስጥ፣ መኪና መቀያየሩን እንደ ኃጢአት ቆጥሮት ይሆናል፡፡
ከጥቂት ቀናት በኋላ ልኡል የተባለ ዘፋኛ ጓደኛየ የኢዮብን በድንገት መውደቅ ሲነግረኝ ወደ ቅዱስ ገብርኤል ሆስፒታል ሄድኩ፡፡ዘፋኞችና አዘጋጆች መጠበቂያው ክፍል ላይ ተደርድረው ይተክዛሉ፡፡ዘሪቱ፣ዳግማዊ አሊ፣እቁባይ በርሄ፣አጃቸውን አገጫቸው ላይ ጭነው፣ተቀምጠዋል፡፡የኢዮብ ባለቤት ወድያ ወዲህ እየተንቆራጠጠች ታነባለች፡፡
ዛሬ ደግሞ ይሄው ሞቱን ሰማሁ፡፡ለካ፣ወደ ደሴ የሚሄደውም አውቶብስም ሆነ፣ሌክስ ፕላዛ ሕንጻ ስር፣ የቆመው ቪታራ መኪናው መዳረሻቸው አንድ ነው፡፡መቃብር!!
ኢዮብ!!! በጠፈሩ ውስጥ፣ ያለ ግብ ከሚዞሩ ኮረቶች፣ያለ ምክንያት ከሚበሩ ኮከቦች በቀር ምንም የለም ብየ እንደማምን ታውቃለህ፡፡ይሁን እንጂ ለዛሬ እንኳ፣ የኔ እምነት ከሽፎ ያንተ እምነት እውነት እንዲሆን እመኛለሁ፡፡በምድር ለገጠመህ መራራ እጣ ሰማያዊ ካሳ(ጉማ) እንድታገኝ እመኛለሁ፡፡

የኢሳት የውይይት መድረክ ከየት ወዴት!!?

$
0
0

ethsat ይህ ርዕስ እጅግ ሰፊ በመሆኑ በቀጣይነት ብዙ ልንወያይባቸው የሚገቡ ሃሳቦችን ይጠቁማል፤ እኛም ለወደፊት በዚህ ጉዳይ ዙሪያ ብዙ የምንል መሆኑን ከወዲሁ ማሳወቃችን አስፈላጊ ነው። ስለሆነም ለመንደርደሪያነት ይጠቅም ዘንድ ለዛሬ ሃሳባችንን ባጭሩ እንደሚከተለው ጠቆም አርገን ማለፍ ግድ በመሆኑ አነሆ እንላለን።

[የኢሳት-የውይይት-መድረክ-ከየት-ወዴት.pdf"]

እዬገደለ የመጣ ቅጥረኛና ፋሽስት ኃይል የሚኖረውም እየገደለ ነው። (እምብኝ በል-ጎፍንን )

$
0
0

እምብኝ በል-ጎፍንን                             

 እዬገደለ  የመጣ ቅጥረኛና ፋሽስት ኃይል የሚኖረውም እየገደለ ነው።

Yekofelewየሰው ልጅ ህይወት እጅግ በጣም ውድ ነው በድሮው ጊዜ የሰው ልጅ ሕይወት ይቅርና ሰው የሚመገባቸው እንሥሣትም ሊታረዱ አንዳንድ ቅድመ ዝግጅቶች ሲደረጉ ቡናው ሲፈላ እጣኑ ሲጨስ ጮፌው ሲነሰነስና ሊታረዱ ሲቀርቡ አራጁ በተወሰነ ደረጃም ቢሆን  በአዕምሮው ላይ ሥነ-ልቦናዊ መረበሽ እንደሚፈጥርበት ይታመናል። የለየለት ደም አፍሳሽ ከሆነ ግን ይህ ላይከሰት ይችላል። ታራጆቹ እንሥሣትም በአራጃቸው ወይም በገዳያቸው እጅ ሲገቡና ሲታሰሩ ጭንቀትና መረበሽ ሊኖር እንደሚችል እገመታለሁ። ሕይወት አንዴ ካለፈች አትመለስምና ከባድ ጫና ያሳድራል ነገሮች ሁሉ ይጨልማሉ ይህ ግን የሚሆነው ፈሪሃ እግዚአብሔር በልቡ ላደረበትና አርቆ ለሚያስብ ብቻ ነው። ለአረመኔዎቹና አምባ-ገነኖች ይህ በፍጹም አይገባቸውም።

በሰው ልጅ ላይ የሚፈፀሙ የግድያ ሁኔታዎችን ስንመለከት ዘርፈ ብዙ ሆነው እናገኛቸዋለን።-በሕግ ዓምላክ በሚባልበትና የሕግ የበላይነት ባለበት አገር በሰው ልጅ ላይ ሞት የሚፈረደው ተከሳሹ ወንጀል መፈጸሙ ታምኖበት በፖሊስ ተይዞ በአቃቢ ሕግ ክስ ተመስርቶበት ፍርድ ቤት ቀርቦ የፈጸመው ወንጀል በማስረጃ ከተረጋገጠ በኋላ የፍርድ ውሳኔዎች ይተላለፋሉ ወንጀሉ በሞት የሚያስቀጣ ከሆነ ዳኛው ወይም ዳኞች የሞት ፍርድ እንዲበየንበት ያደረገውን የወንጀል አፈጻጸም ድርጊትና ምክንያት በዝርዝር ከሕጉ ጋር እያገናዘቡ ካስረዱና ብዙ ተመልካችን እንዳያስደነገጥ ጥንቃቄ በማድረግ ወይም ዝግ በሆነ ችሎት በወንጀለኛው ላይ የሞት ፍርድ ይፈጸምበታል። ይህ እርምጃ የሚወሰደው የአካባቢውን ሕዝብ ደህንነት ለመጠበቅ ፤ሰላም እንዲሰፍንና የተረጋጋ ለማድረግ ዳግም የዚያ አይነት ወንጀል እንዳይፈጸምና ሕብረተሰቡ በሥነ-ምግባር የታነጸና በሕግ የሚገዛ እንዲሆን ለማድረግ ፤ የወንጀል መፈጸም ተግባርን እንዳይስፋፋ ጤናማ ሕብረተሰብ ለመገንባት የሚወሰድ የመንግሥት እርምጃ ነው። የፖሊስ ፤ አቃቢ-ሕግና የዳኛ ተግባሮች በፍጹም የማይለያዩ ተያያዥነት ያላቸው ሲሆን የአንድን ማሕበረሰብ ደህንነት ፤ ሰላምና ፀጥታ እንዲሰፍን ለማድረግ ደረጃ በደረጃ በየተቋማቸው ማድረግ የሚገባቸውን ፈጽመው መገኘትና አንዱ ሌላውን እያገዘ በጋራ የሚሰሩት የተቀናጀ የሥራ ውጤት ግቡን ይመታል።

ግለሰቦች ከሕግ በላይ በሆኑበትና በሕግ ዓምላክ በማይባልባቸው እንደ ኢትዮጵያ ባሉ አገሮች የሚኖረው ግድያን ወስደን ስንመለከት ደግሞ ሁኔታዎች ቦታቸውን ለቀው በግልባጩ እናገኛቸዋለን። ከዚህ በታች ስማቸውን የጠቀስኳቸው አገር መሪዎች በዓለም ላይ እንዲታወቁ ያደረጋቸው ተግባር ምን እንደሆነ አንባቢዎቼ በግልጽ የሚረዱት እንደሚሆን አምናለሁ። «ዘለው ኦፍ ጃንግል» (the law of jangle )«የጫካ ሕግ» በሚል የተፃፈች ትንሽ መጽሐፍ አንድ ወቅት ላይ አንብቤ ነበር። ያች ትንሽ መጽሐፍ ያዘለችው መልዕክት ሕግ ለምን እንደሚወጣና ጠቀሜታው ምን ያህል እንደሆነ ያሳደረብኝ ግንዛቤ እስከ መቼውም አይረሳኝም።መጽሐፏ በጫካ ስለሚኖሩ የዱር አራዊት(እንሥሣት) ህግ አለመኖርና ጉልበታሙ ወይም ጉልበታሞች ተባብረው ጉልበት የሌለውን አስገድደው ገድለው ተመግበው እንደሚያድሩና እንደሚውሉ እንደሚኖሩ ግልጽ አድርጋ ታሳያለች። በሩዋንዳ ፤ካሞቦዲያ እንዲሁም እስከ አሁን ድረስ ትኩሳቱ ባልበረደው ሶሪያ የምንሰማውና የምንመለከተው በዘረዘርኳቸው አገሮች የተካሄደውና እየተከሂያደ ያለውን ስንመረምር በምን አይነት መርህ እየተጓዙ እንደሆነና ጨካኞችና አምባገነኖች የሚፈጽሙትና የፈጸሙት ተግባር  ከጫካው ሕግ ያልተለየና አረመኔያዊ ተግባር መሆኑን ቁልጭ አድርጎ ያሳየናል።

አገርንና ዳር ድንበርን ለማስከበር ይሞታል፤ በሀሰት በፍርደ ገምድል ዳኛ ተፈርዶም ይሞታል፤ ሲሰርቁና ሰው ሊገድሉ ሲሞከርም ይሞታል ፤ በትንታም ይሞታል ፤ሌባ በረት ሲከፍት ፤ ከባለትዳር ሴት ሲልከሰከሱም ይሞታል፤ የሰው ቤት ሲበረብሩም ይሞታል፤ በሕመምና እድሜ ሲደርስም ይሞታል የሰው ልጅ ሕይወት ማለፊያዋ መንገድ ብዙ ነው። የእኔ መነሻ ግን ይህ አይደለም ሥልጣን ለመያዝና ከያዙ በኋላም ጨካኝና ነብሰ ገዳይ ሆነው ለመቀጠል የሚያስቡ አርመኔዎችን አስመልክቶ ትንሽ ለመግለጽ ያህል ነው። በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ የዘውዳዊ አገዛዝ ዘመን የ1966ቱ የየካቲት የሕዝብ አልገዛም ባይነት ለማንበርከክ የተወሰዱትን እርማጃዎች ፤ቀደም ሲል በአርሲ ፤በጎጃምና በትግራይ የአርሶ አደሮችን ሕዝባዊ እንቅስቃሴ ለማፈን የተደረግውን እርማጃ ፤በደርግ የወታደራዊ አገዛዝ ዘመን ለመገንጠል በተነሱ ጎጠኞች(ጠባብ ብሔረተኞች) የተወሰደው ፤አዲስ ሥር ዓት እንገነባለን ብለው በሕብረ- ብሔር ድርጅት ተቃውሞ ያነሱትን ትግል ለመበተን የተደረገውን ጥቃት ፤ህወሃት ከኤርትራ ጋር በጫረው ጦርነት የያለቁት የሁለት ወገን ትውልዶችና፤ «ራስ ሳይጠና ጉተና እንዲሉ» ወደ ሶማሊያ ሄደው ያለቁት ኢትዮጵያውያን ፤ ወደ ሩዋንዳ ፤ኮንጎ፤ ኮርያ የሄዱት ኢትዮጵያውያን ፤ ህወሃት ከበርሃ ጀምሮ በስውር የፈጀው ታጋይ የትግራይ ወጣት ፤ በቀን በአደባባይ መሠረት በሌለው ቂመኝነት የተገድሉት ኢትዮጵያውያን አሁንም በሰበብ አስባቡ እተጨፈጨፉ የሚገኙት ዜጎቻችን ሕይወት ቀጠሮ ተይዞለት በአዲስ ዓመት ይመለሳል የሚባል እንዳልሆነ ሁላችንም እናውቃለን ። በደርግ ጊዜ ደርግ ሕዝቡን ፈጀው እያሉ ነፍጥ አንስተው የተንቀሳቀሱት የዛሬዎቹ ገዥዎቻችን ለምን ሕዝባችን ይጨፈጭፋሉ?ወይስ ከጌታ ትእዛዝ ወርዶ ተፈቅዶላቸው ነው?ደርግ በሕዝብና በቀድሞ የቀዳማዊ ኃይለሥላሴ ባለሥልጣናት ላይ ኢ-ፍትሃዊ እርማጃ ወሰደ ያ አስፈሪ ሞት በራሱ ላይ መጣ። ህወሃት ከዚያ አስፈሪ ሞት የሚያመልጥበት ምን ብልሃት አገኘና ነው እንዲህ በእብሪት ተወጥሮ ሕዝብን በጅምላ የመጨፍጨፍ ተግባሩን እንደ ሰደድ እሳት እያቀጣጠለ ያለው? ግራኝ መሐመድ የእስልምና ሃይማኖት ተከታይ ነበር በውጭ ድጋፍና እርዳታ  በክርስቲያን ሕዝባችን ላይ ጨካኝ ጭፍጭፋ እንዳደረገ ታሪክ ዘግቦት አልፏል ። ቶርኮች ፤ ግብጾች እንዲሁም በዓረቦች ድጋፍ በሱዳን መሐዲስቶች(ድርቡሽ) እየተባለ የሚታወቀው በተመሳሳይና በተደጋጋሚ በክርስትና እምነት(በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሀዶ ሃይማኖት) ላይ ዘምተው አልተሳካላቸውም።ኢትዮጵያዊ  የእስልምና እምነት ተከታዮችን እስላማዊ መንግሥት ሊያመጡብህ ነው ብሎ ሕዝብን ማስፈራራትና የማከፋፈል ዘመቻ ማካሄድ የት ሊያደርስ ነው? ለመሆኑ ህወሃት ምንስ እምነት ኖረውና ነው እስላማዊ መንግሥት  ክርስቲያናዊ  መንግሥት እያለ ሊሰብከን የከጀለው ? ይህ ከንቱ ውዳሴ ነው። ስለዚህ ሕዝቡ ጀሮውን ሊሰጥ አይገባውም ባይ ነኝ። መጀመሪያ የዜጎችን መብት ማክበር ይቅደም።የቻይና ባለሀብቶች ኢትዮጵያዊ ዜጎችን ተወልደው በአደጉበት እትብታቸው በተቀበረበት በአጥቢያቸው በአገራቸው ምን እየሆኑ  እንደሆነ የሚያውቀው ህወሃት ዜጎቼ ተደፈሩ ብሎ ለምንስ እርምጃ አልወሰደም ? ከዚህ በላይ መርከስና መውረድ የበለጠ ምን ሊመጣ ይችላል?  አቶ በረከት እናቱ ሲቀበሩ መድፍ እንዲተኮስላቸው አስደርጓል እናቱ ቢሞቱ እህት እንኳ የለውም የሚያዝን ልብ? እግዚአብሔር ያሳያችሁ!! እውን እኒህ ጠይም ደማማ እናት እንዲህ ተፈንክተው ደማቸውን እያዘሩ እንዲሄዱ ማድረግ ይገባል ? ምን አይነት ሥልጣኔስ ሊባል ነው? አሁን እኒህ እናት ጠቅላይ ሚንስቴር ለመሆን መንግሥትን ለመፈንቀል እያሸበሩ ነው? እንዲህ የተቀጠቀጡት? ኢትዮጵያ አገራቸው አይደለችም ? ወይስ ኢትዮጵያዊ መሆን የግድ ካልተቀጠቀጡና ደማቸውን እያዘሩ ካላሳዩ (ካልታዩ) ኢትዮጵያዊ ዜግነት አይገባቸውም ?ኢትዮጵያ እኮ የሁላችን አገር ናት። እንዴት ኢትዮጵያዊ ሆኖ ኢትዮጵያዊ እናቱን ደም እያዘሩ እንዲሄዱ ያደረጋል? ምን አይነት ሰው በላ ሥርዓት ነው የተፈጠረብን? ለመሆኑ ይህ በህወሃት ዘመን ተወልዶ በህወሃት የታጠቀ የአጋዚ ነብሰ በላ ጠመንጃ አንጋች ኃይል  እናት እህት ሚስት ይኖረው ይሆን ? ሴቶችን እንደ ፊውዳሉ ሥርዓት ማናናቄ አይደለም እኒህ እናታችን ሴትና በእድሜ ጠና ያሉ ናቸው በምን ሂሳብ ነው የተደበደቡት በምን ምክንያት ነው ደማቸው እንዲፈስ የተፈረደባቸው? ይህ የህወሃት አጋዚ ሠራዊት አደብ የሚገዛውና ለሕግ የሚገዛው መቼ ነው ?እኛ ኢትዮጵያውያንስ መቼ ነው እንደበግ እየተጎተትን ከመታረድ የምንድነው? ድምፃችን ይሰማ በማለት ሁለት ዓመት አንዲት ጠጠር ሳይወረውሩ፤አንዲት ቅጠል ሳይበጥሱ የእምነት ነፃነታችን ይከበር ብለው ጥያቄ ስለአቀረቡ ችግሩ ምኑ ላይ ነው? መልሱን መስጠት ወይስ እያፈሱ ማጎርና መደብደብ በጥይት መቁላት? ኧረ እናስተውል ጎበዝ እስከ መቼ ነው ቀን እንዲህ ሊገፋ የሚችለው ?አሸባሪውስ ማን ሆነና ነው? አሸባሪ የሚሉት ለእምነታቸው ነፃነት የሚታገሉትን ነው ወይስ ከነዚህ ለእምነት ነጻነት ከሚታገሉት ኢትዮጵያዊ እስላሞች ውስጥ ሰርጎ የገባ አለ በሚል ነው ? ሰርጎ የገባ ካለ ለይቶ ማውጣትና በሕግ እንዲቀጣ ማድረግ የማን ተግባር እንደሆነ ከጠፋቸው እውነትም ጠፍተዋል ማለት ነው ቢጠፉም ይሻላቸዋል።

እየገደለ የመጣ ፋሽስታዊ ኃይል የሚኖረውም እየገደለ ነው።  ያልኩበት አብይ ምክንያት ህወሃት በወርሃ የካቲት 1967 ዓመተምህረት እንደ ድርጅት ከመቆሙ በፊት የተለያዩ መጠሪያዎችን ይዞ ይንቀሳቀስ የነበረ ሲሆን በመጨረሻ ህወሃት በሚለው ስም ጸንቶ ሲቀጥል ከቀን አንድ ቀን ጀምሮ በሰው ግድያ የተጀመረ የራሱን አባላት ሳይቀር እየበላ ያደገ ድርጅት ሲሆን 17 ዓመት ደርግ ሥልጣን ላይ በነበረበት ወቅት 22ዓመት መላ አገሪቱን ከወረረ በኋላ ጊዜውን ያሳለፈው ሰው በመግደል ነው። ሰው መግደልና በደም መጠማት ደግሞ በሕክምና ሊድን የማይችል በሽታ መድኃኒቱ በመሰል እርምጃ(አክሽን )ሊወገድ የሚችል ከቫይረስ የከፋ በሽታ ነው። ህወሃቶች የፈለገው ብዛት ያለው ሰው ይሙት አንድ ሰው ይሙት ቅንጣት ታህል አይሰማቸውም የሚሰማቸው የሰው በላው ሥርዓት አስከባሪ ወይም እንደ አበደ ውሻ የሚክለፈለፈው አንጋች ሲሞት ብቻ ነው። ሰው የገደለ እኮ አዩኝ አላዩኝ ብሎ ራሱን ለመሸሸግ መታገል አለበት።እንዴት ሰው ገድሎ ታማኝነቱን ማስመስከር እንደ ዝና ተቆጥሮ ይሳለቁብናል? ቤተመንግሥታችንስ እንዴት የነብሰ ገዳዮች መናኻሪያ ይሆናል?እየገደሉን መጥተው እንዴት እየገደሉን እንዲኖሩ እድሉን እንሰጣቸዋለን? ስማቸው ተቆጥሮ የማያልቅ ወንዝ የማያሻግሩ የተቃዋሚ ድርጅቶች ወይም ከአውሮፓና  አሜሪካ ሄዶ ኢትዮጵያውያንን ከህወሃት የአፓርታይድ አገዛዝ ነፃ ሊያወጣ የሚችል እንደሌለ እንቅጩን እንነጋገር ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በወጣት ኢትዮጵያውያን የሚመራው ሰማያዊ ፓርቲና አሁን ከእንቅልፉ የባነነው የአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲን እንደ አንድ ግኝት እንደ አንድ ርምጃ እንውሰድና ትግሉን አጋግሎ መቀጠል ያለበት ሲሆን ከዚያ ባሻገር ያለው ግን መድሕሃኒቱ ያለው ከየሁላችን እጅ ነው ። እምብኝ አልገዛም ማለት ፤ ፍርሃትን ማስወገድ ፤ ራስን ነፃ ለማውጣት መታገል ፤መደራጀት ፤ አንድነት መፍጠር የህወሃትን ሰርጎ ገቦችና ሰላዮችን ማዋከብና ማጋለጥ ፤የሚሠሩት ጸረ-ሕዝብ ተግባር ህወሃት በአማራ እናትና እህቶቻችን ላይ የሚያመክንና የአማራውን ሕዝብ ቁጥር ዝቅ እያደረጉ ከሁሉም አካባቢ እያፈናቀሉ እየገደሉ ዘሩን ለማጥፋት የሚያደርጉትን ድርጊት በቀጣይነት ማጋለጥ በርን ከፍቶ አለማስገባት…ወዘተ እንጅ እንደ ብሉይ ኪዳን ቀኙን ሲመታህ ግራውንም ስጠው ወይም በየተራ እንደ ዓመት በዓል በግ እየተጎተቱ መታረድና በየከርሸሌው እየገቡ በፈላና በቀዝቃዛ ውሃ መቀቀል በሌባ ጎማ ተዘቅዝቆ መገረፍ፤ በኤሌክትሪክ ሽቦ መጠበስ ፤በሴትና በወንድ ብልት ወስጥ አሰቃቂ ተግባር በመፈጸም የገደሉትን ሰው ዘቅዝቆ ማንጠልጠልን በመኪና መጎተት በደርግ ጊዜ ከነበረው በሚበልጥ ሁኔታ መዋረድ እንዴት እንዲቀጥል እድሉን እንሰጣቸዋለን? እኛም ቤት እሳት አለ መባል አለበት። ነፍጥ ወይም ጠመንጃ አንግቶ የሚንቀሳቀስ ኃይል ካለም የህወሃትን የመከላከያ ሠራዊት በተገኘው አጋጣሚ ሁሉ ማዋከብና ቢያንስ ወደ ሕዝብ ያዞረውን መሣሪያ እንዲያነሳ ማድረግ፤ በህወሃት ፖሊስ ፤ ደህንነትና የመከላከያ ሠራዊት፤በካድሬው ላይ የመበተን ወይም በውስጡ ያለው ቅራኔ እንዲባባስ የፕሮፓጋንዳ ሥራ አዘውትሮ መሰራት አለበት ወደዚህ ለመግባት የሚያስችሉ ብዙ ክፍተቶች አሉ በፖሊስና በመከላከያ በደህንነት ውስጥ ከላይ እስከ ታች ያለው መዋቅር የተያዘው ከአንድ ጎሳ በመጡ ስለሆነ ሌላውን ለማነሳሳት ለም ሆኖ ያለ ነጥብ ነው። በግንባሩ በውስጡ የተፈጠረውን የእኔ እቀደም እኔ ሽኩቻም እንዲባባስ መገፋፋት ይገባል በተጨባጭ ያየነው የግንባሩ አባላት ባኮረፉ ቁጥር እንዳያፈነግጡ ተሰርቶ የማያውቅና ራሱ ባወጣው ሕግ ላይ እንኳን ያልሰፈረ 3 ጠቅላይ ሚንስቴር ወዘተ…የፖለቲካ ሥልጣን ከችሎታና ከአቅም ብቃት የተመዘነ ሳይሆን ላለመቀያየም የሚደረገው ጥረት ውስጡ ምን ያህል የነኮረና የበሰበሰ እንደሆነ ስለሚያሳይ ይህን መጠቀም ያሻል። በግብር የሚሰበሰበው ገንዘብ ገቢ እንዳይሆን ማድረግ ፤ ከውጭ የሚገኘውን እርዳታ እንዳይሰጥ ማድረግ  በማንኛውም አይነት መንገድ የሚገኘው ገቢ ለአገር እድገትና ልማት ሳይሆን የሚውለው የህዳጣኖችን ከርስ መሙያና ፍላጎት ማስተናገጃ እንጅ ለሕዝብ ብሶትና ችግር ስለማይውል ይህን በጡንቻው የሚያምን ኃይል ለማሽመድመድ ኢኮኖሚያዊ አቅሙን እንዲወርድ ማድረግ ማዳከም ገበሬው ፤ነጋዴው ፤ ሌላው ግብር ከፋይ አልከፍልም እንዲል ማድረግ ያስፈልጋል። ተተኪ ትውልድ እንዳይኖር የተስማሙ ጭፍኖችን በማሳከም በሕብረት ለአንዲት ኢትዮጵያና ለአንድ የኢትዮጵያ ሕዝብ በሁሉም አይነት ዘርፎች መስዕዋትነት መክፈል ይገባናል። ኢትዮጵያ ተተኪ ትውልድ እንዳይኖራት የማድረጉ ዓላማ የማን እንደሆነ አስፈፃሚው ማን እንደሆነ እንተዋወቃለን። ዛሬ ኢትዮጵያዊ መሆንን የጠሉና ኢትዮጵያ የገጠማትን ችግር ላለመጋፈጥ ታሪክን ሸምጥጠው የካዱ ሁሉ ፈጥነው ችግራቸውን ቢያስተካክሉ ይበጃቸዋል። አዎ ኢትዮጵያ አሁን ከራስዋ በበቀሉ የአገር ውስጥ ጣሊያኖችና ከውጭ እንግሊዝና ጣሊያን አጥልተውብን በሄዱት የመከፋፈልና የእርስ በርስ አለመተማመን ምክንያት ችግር ገጥሟታል ።ነገር ግን በቅርቡ ኢትዮጵያ የኢትዮጵያውያን ኢትዮጵያ ትሆናለች። ያኔ ታዲያ እነዚህ የእናት ጡት ነካሾችና የበሉበትን መሶብ የደፉ የአገር ውስጥ ጣሊያኖች ጀንበር ትጠልቅባቸዋለች፤አንገታቸውን እንዲደፉ የግድ ይሆንባቸዋል።ለሆዱ ያደረው የሚበዛ ቢሆንም እውነቱ የት ላይ እንዳለ መርምረው ያወቁ ወይም የሚያውቁ በዚህ ሥርዓት ውስጥ ስለሚገኙ ምርቱን ከገለባው የመለየት እንቅስቃሴም ሊሰራ ይገባል።የራስን ደጋፊ ኃይል በየተቋሙ መፍጠር ካልተቻለ መሣሪያ አምላኪ የሆነው ቡድን የውስጡን ቅራኔ ጋብ በማድረግ ነገሮችን በመለጠጥ የተለከፈበትን ወረርሽኝ ወደ ሌላው እያላከከ እድሜ ለመግዛት ስለሚችል የዚህ ዓይነቱን እድል አለመስጠትና በሩን መዝጋት አስፈላጊ ነው ብቻ ሳይሆን በጣም ጠቃሚ ነው። ሥርዓቱ መበስበሱን ለማየት ሩቅ መሄድ አያስፈልግም የአማራው ነገደ ብሔር ዘሩ እንዳይራባና ቁጥሩ እንዲቀንስ የተደረገው ፀረ-ሕዝብ ተግባር ቀላል አይደለም ነገር ግን ምሥጢሩን ደብቆ ለመያዝ አለመቻል ዋና ምልክት ነው። አሁንም ይህን ትኩረት ሰጥቶ ቢቀሰቀስበትና ለዓለም ሕብረተሰብ እንዲደርስ ቢደረግ አንዳንድ ጤናማ የሆኑ አገሮች ድጋፋቸውንና ግንኙነታቸውን ስለሚያቋርጡ ሥርዓቱ ብጥስጥሱ የሚወጣበት ጊዜ እየፈጠነ እንዲሄድ ያደርጋል። የታሰሩ ጋዜጠኞች የፖለቲካ ድርጅት አባላት እነአንዱ ዓለም አራጌ (የሕሊና እስረኞች) የታሰሩበትን መርምሮና ግልጽ አድርጎ ማቅረብ አንዱ የማጋለጥ ሥራ ተሰራ ማለት ነው። ክቡር አምባሳደር እምሩ ዘለቀ እንደጻፉት ሳይቦዝኑና ሳይሰላቹ በተቻለው መንገድ ሁሉ ሥርዓቱን ማዋከብ ያስፈልጋል።

(Adolf Hitler German-Rodolfo Graziani Italy– Joseph Stalin Soviet Union -Omar Hassan al-basher Sudan–Mengistu Haile Mariam- and Meles Zenawi in Ethiopia)

                ራዶልፍ ሂትለር በጀርመን አገር የሚኖሩ ይሁዳዎችን ጨረሰ ፤ አዶልፎ ግራዚያኒ አውሮፓን አቋርጦ ባሕር ተሻግሮ በአፍሪካ ምድር የቅኝ ተገዥ አገሮችን ለማስፋፋትና ሀብታቸውን ለመዝረፍ ወደ ኢትዮጵያ አቅንቶ ሕዝባችን ጨረሰ ፤ጆሴፍ ስታሊን የብላድ ሚር ኢሊችን ሥልጣን ከተረከበ በኋላ እንደ ሬድ ተረርና የስታሊን ዱላ በሚል የራሱን ሕዝብ ጨፈጨፈ ፤ የሱዳኑ ኦማር ሀሰን አልበሽር ከዐረብ ጋር ያልተዳቀሉትን የደቡብ ሱዳንን ሕዝብ ፈጀ ፤ ዝሃና ግራውን መለየት የተሳነው መንግሥቱ ኃይለማሪያም በቀይ ሽብር ሁሉም ነገር ወደ ጦር ግንባር እያለ ተኪ የማይገኝለትን ወጣት ምሁር ሠራተኛ ፤ አርሶ አደር ፤ የከተማ ነዋሪ ፤ ነጋዴ  አዛውንት ጨረሰ የኤርትራን ተቃዋሚዎች በኃይል ለማንበርከክ ሞክሮ የመገንጠል እድል እንዲታደሉ አደረገ ። ሌላው የአገር ጉድና አረም የምዕራባውያንና የዐረቦች አሽከር አያት ቅድመ አያቶቹ የጣሊያን አባሽ አጎንባሽ ሹምባሽና ለባሽ የነበሩት ልጅ  በነ-ስብሃት ነጋና አባይ ፀሐየ አጆሃ! እየተባለ የሻእቢያን የመገንጠል ዓላማ ነዳጅ ሆኖ አገለገለ ኢትዮጵያን ወደብ የሌላት አገር አደረገ ፤ አብዛኛውን ከውጭ አገር የሚያዋስነውን የአገሪቱን ለም መሬት ለባዕዳን በረከት ሰጠ ፤ ሊበርድ የማይችል የጎሳና የሃይማኖት ግጭትና ጦስ አቀጣጥሎ በአበበ ገላው (አንድ ጋዜጠኛ ወቀሳ) ምክንያት በ30 ሰከንድ ውስጥ በድንጋጤ ርዶ ያለቀኑ የተቆረጠ ቅጠል መስሎ እኛን ረመጥ ውስጥ ከቶ ከማይጠየቅበት ዓለም ተጓዘ ያ ሚፈራውን ሞት ሞተ። መለስ ዜናዊና ድርጅቱ ህወሃት ነፍጥ ያነሱት የትግራይ ሕዝብ በሁሉም አይነት መንገድ ተበደለ ብለው እንደሆነ አድርገን የምንረዳ ልንኖር እንችላለን። የዛሬውን አላውቅም እንጅ ህወሃት የትግራይ ወላጆችን ጨርሷል።የተረፉትን ጧሪ አልባ አስቀርቷል፤ተኪ የማይገኝለት ወጣት ትውልድ በልቶ ያደገ ድርጅት ነው።በርግጥ በሥርዓቱ ዙሪያ ያሉት ሚሊየነር ሆነዋልከሚገባው ብላይ ከበርዋል ። የትግራይ ሕዝብ ግን በሳውዝ አፍሪካ እንግሊዞች ካራመዱት የአፓርታይድ አገዛዝ ሊመሳሰል የሚችል ሲኦል ውስጥ ገብቶ ነው የሚገኘው።በቅርቡ አንድነት ለፍትሕና ለዴሞክራሲ የሚሊዮኖችን ድምጽ ለማሰባሰብ በጀመረው ዘመቻ መቀሌ ላይ በክልሉ ገዥዎች የተደረገውን ሰምተናል።ትግራይ ውስጥ ወይን ከሚለው የህወሃት ጋዜጣና ከህወሃት ራዲዮ አልፎ ዜና ማድመጥና ማንበብ ወይም በሌላ አነጋገር ሌሎችን ጋዜጦችና መጽሔቶች አይገቡም የመገናኛ ብዙሃንን መስማት የሚያስቀጣ እንደሆነ ይታወቃል።የትግራይ ህዝብ ከሌሎች ኢትዮጵያውያን ጋር በመሆን ይህን እሥራት ሰብሮ መውጣትና መብቱን ማስከበር ይገባዋል።

በመጨረሻም በአይነቱ የመጀመሪያ የሆነው በኢትዮጵያ ራዲዮና ቴሌቪዥን አገልግሎት አስተዳደር ክፍል አዘጋጅነት በ18/08/2013 ዋሽንግተን አርሊንግተን የሚካሄደው የታዋቂ ግለሰቦች ፤ የፖለቲካ አክቲቪስቶች ፤ የሃይማኖት መሪዎችና የተቃዋሚ ድርጅቶች ፤ የስቪክ ማህበራትና ሌላውንም ያካተተው ስብሰባ ለኢትዮጵያ ህዝብ ትልቅ የምሥራች ይዞ ብቅ እንደሚል ተስፋ አደርጋለሁ። ለሁሉም ግን የማሳስበው ቢኖር ሰጥቶ መቀበል ፤ መናበብ ፤ መደማመጥ ፤ መከባበርና ፍቅርን መተሳሰብን የሚያጎናጽፍ እንዲሆን መልካም አርአያ ሆናችሁ እንድትገኙ ነው።

ኢትዮጵያ በክብር ለዘልዓለም ትኑር!!!

ዋስትናችን እርቅ ብቻ ነው!

$
0
0

“እኛ የእሳት አደጋ ብርጌድ የለንምና ዋ!!” ኦባንግ
በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ


peace roconእሳት ሲነሳ የመጀመሪያው ተግባር እሳቱን በፍጥነት ማጥፋት ለሚችለው የእሳት አደጋ ብርጌድ መደወል ሲሆን፣ ቀጣዩ ተግባር እሳቱ በተነሳበት አካባቢ ያሉ ነዋሪዎች ነፍስ አትርፈው እሳቱን በተገኘው መንገድ ለማጥፋት መረባረብ ነው። ይህ የተለመደው ተግባር ዛሬ በኢትዮጵያ ስለመስራቱ የአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ /አኢጋን/ ዋና ዳይሬክትር ስጋት አላቸው። እናም “እኛ የእሳት አደጋ ብርጌድ የለንምና ዋ!!” የሚል ማስጠንቀቂያ አዘል ጥሪ ያሰማሉ።

“አሁን ባለው ተጨባጭ ሁኔታ እሳቱ ፊትና መልክ ይዞ ሲቀጣጠል አላነውም እንጂ በርካታ የማቀጣጠያ ቅመሞች ተዘጋጅተውለት ለመንደድ በዝግጅት ላይ ነው። መንደዱ የማይቀረው ይህ እሳት ቢነሳ የሚያጠፋው የለም” የሚሉት አቶ ኦባንግ ሜቶ፣ ጥላቻው በሰፈር ደረጃ ከርሯል ይላሉ። በየመንደሩ ህዝብ እንዲቧደን ተደርጓል። ሚና ለይቷል። አገር የሚመራው መንግሥትም ችግሩን ከመፍታትና አገሪቱን ከስጋት ከማላቀቅ “ጥሪ አይቀበልም” በሚል የሃይል ርምጃ መምረጡ ነገሮችን ይበልጥ እንዳወሳሰበ ይናገራሉ።

በየአቅጣጫው ያሉ ወገኖች ቆም ብለው ሊደበቁት ከማይችሉት ከህሊናቸው ጋር ሊነጋገሩ እንደሚገባ ያመለከቱት አቶ ኦባንግ “ግብጾች ግብጾችን ገደሉ፣ ገና ቀውሱ ይቀጥላል። ይህ እጅግ ዘግናኝ የሆነው ቀውስ እኛ ዘንድ ሳይደርስ ወደ እርቅ እናምራ። ለእውነተኛ እርቅ ጊዜው አሁን ነው” በማለት አንገብጋቢ ያሉትን ጥሪ ያስተላልፋሉ።

“ላለፉት 22 ዓመታት ኢትዮጵያ ላይ ከየአቅጣጫው የተረጨው መርዛማ ፖለቲካና፣ ሰብአዊነት የጎደለው አስተዳደራዊ መዋቅር የፈጠረው ውጥረት ወደ መፈረካከስ እየነዳን ነው” በማለት የስጋቱን መጠን የሚጠቁሙት አቶ ኦባንግ ፣ በግብጽ የተፈጠረው ቀውስ በሃይል ሊቆም የማይችልበት ደረጃ ሲደርስ ምዕራባዊያንም ሆኑ አሜሪካ የሃዘን መግለጫ ከማውጣት የዘለለ ስራ አለመስራታቸው ለኢትዮጵያዊያን ታላቅ ትምህርት ሊሆን እንደሚገባ ያሰምሩበታል።

በሩዋንዳ ለቁጥር የሚያዳግቱ ሰዎች አልቀዋል። በኮሶቮ ህዝብ ተጨፍጭፏል። ዳርፉር ንጹሃን የጥይት ራት ሆነዋል። ይህ ሁሉ ከመሆኑ በፊት ሃያላን መንግስታትና “ድርጅቶቻቸው” በእነዚህ አገራት ውስጥ ነበሩ። እያወቁት ነው የሆነው። ግን ጉዳዩ የጥቅም ችግር ስለማይፈጥርባቸው አገራቱ በደም ጎርፍ ሲታጠቡ በዝምታ ተመልክተው እንደነበር ያስታወሱት አቶ ኦባንግ፣ “ሶሪያ ስትፈርስ፣ ከ100 ሺህ ሰው በላይ ሲያልቅና አሁንም እያለቀ ባለበት ሁኔታ እልቂቱን ማስቆም እየቻሉ ዝምታን መርጠዋል” በማለት አቶ ኦባንግ ከነዚህ አገሮች፣ በተለይም “አሁን ግብጽ ላይ በተፈጠረው ችግር ካልደነገጥንና ለሚቀርበው የእርቅ ጥያቄ መልስ ለመስጠት የማንዘጋጅ ከሆነ አደጋው የከፋ ሊሆን ይችላል” ሲሉ አስጠንቅቀዋል።

ጥያቄው የስልጣን ሳይሆን አገሪቱ ላይ ያንዣበበውን የሞት አደጋ የመግፈፍ አንደሆነ፣ ይህ አሁን ያንዣበበው የቀውስ ደመና ባስቸኳይ ካልተገፈፈ መከራው የሁሉም ወገን እንደሚሆን ጥርጥር እንደማያሻው የጠቆሙት አቶ ኦባንግ “ንጹህ ልብናና ንጹህ ህሊና ያላችሁ ውጡ፣ ለእውነተኛ እርቅ እንስራ፣ አገሪቱንም እናድን፣ የእሳት አደጋ ብርጌድ የለንምና እኛው አገራችንን በማስቀደም እንታደጋት” ሲሉ ከወትሮው በተለየ ጥሪ አስተላልፈዋል።

በምርጫ ፕሬዚዳንት ሆነው በዓመጽ መፈንቅለ መንግሥት የተደረገባቸው ፕሬዚዳንት ሙርሲን የሚደግፉ የሙስሊም egyptወንድማማች ፓርቲ ደጋፊዎች ላይ የሃይል ርምጃ ከመወሰዱ በፊት በግብጽ ይህ ችግር ሊደርስ እንደሚችል የወተወቱ ነበሩ። ፕሬዚዳንት ሙርሲ ከስልጣን የተወገዱበት አግባብ ቀውስ ሊያስነሳ እንደሚችል ቢነገርም ሰሚ ባለማግኘቱ ቀውሱ ግብጻዊያንን እርስ በርስ አጋደለ። ግብጾች ግብጾችን ጨፈጨፉ። እስከ ሁለት ሺህ የሚደርሱ ሰዎች የተገደሉበት ይህ ቀውስ እንዴት ሊቆም እንደሚችል ፍንጭ የለም። የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ፣ የሰዓት እላፊ፣ ግድያና እስር ዓመጹን ሊገታው አልቻለም። ይልቁኑም መሳሪያ የታጠቁ ተቃዋሚዎች ግብጽን በጥይት እያመሷት ነው። እየገደሉም ነው።

በኢትዮጵያም በተለያዩ ወቅት የተነሱ የህዝብ ጥያቄዎችን በጸረ ሽብር ህግ፣ በእስር፣ በድብደባ፣ በግድያ፣ በማስፈራሪያና በጡንቻ የማስተናገዱ አዝማሚያ ከእለት እለት መጠናከሩ የሚከፋቸውን ሰዎችና ቡድኖች እያበራከተ ነው። የተፈናቀሉ ወገኖች ተበራክተዋል። በተፈናቀሉና መሬታቸው እየተቸበቸበ ያሉ ወገኖች ምሬት የከፋ ደረጃ ደርሷል። ሚዛናዊ ያልሆነው የአስተዳደር መዋቅርና የኢኮኖሚ ልዩነት የፈጠረው ቅሬታ በቃላት የሚገለጽ አልሆነም። እንደ አቶ ኦባንግ ሁሉ እርቅ አስፈላጊ እንደሆነ በማመን እየሰሩ እንደሆነ የሚናገሩትና ለጊዜው ስማቸውን መግለጽ ያልፈለጉ ታዋቂ ምሁር ለጎልጉል እንደተናገሩት “በአሁኑ ወቅት ጥላቻው ከርሮ ህዝብ በገሃድ ስምና ብሔር እየለየ ፊት ለፊት መናገር ጀምሯል፤ የኑሮው ውድነት፣ የመብት ረገጣው፣ ዕንግልቱ፣ … የጥላቻውን መጠን አደባባይ ላይ እንዲታይ እያደረገው መጥቷል። አገራችን ያለችበት መንገድ አደጋ አለው። እርቅ የግድ ነው” ብለዋል፡፡

እኚህ ምሁር “ኢህአዴግ ውስጥ እርቅ አስፈላጊ እንደሆነ የሚያምኑና አሁን በየአቅጣጫው ያለው ችግር የሚያሳስባቸው ወገኖች ስላሉ እነዚህን ወገኖች በመቅረብ ለእውነተኛ እርቅ ለመስራት ጊዜው አሁን፣ ለዚያውም ሳይረፍድ በቶሎ ሊሆን ይገባል። ይህንን ካላደረግን ሁላችንም እናዝናለን። ይቆጨናል። በቀላሉ ልናልፈው ወደ ማንችልው ጣጣ ውስጥ ሳንገባ እንረባረብ” በማለት ተናግረዋል። አስተያየት ሰጪው በቅርቡ ራሳቸውን ገልጸው አስተያየት እንደሚሰጡ፣ ለጊዜው የተጀመሩ ስራዎችን በነጻነት ለመስራት ሲሉ ራሳቸውን ከመግለጽ የተቆጠቡበትን ምክንያት ተናግረዋል።

“አገር እንደ ሰው አካል ነው። አንድ ቦታ ሲታመም ስሜቱ የሙሉው አካሉ እንጂ የተጎዳው አንድ ክፍል ብቻ አይደለም” በማለት የማጠቃለያ አስተያየት የሰጡት አቶ ኦባንግ፣ የአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ ሲቋቋም ዓላማው ሁሉም ነጻ የማውጣት ታላቅ ዓላማ አንግቦ በመሆኑ በዚህ ረገድ በቅርቡ የእርቅ ተግባሩን ሊከውን የሚያስችለውን እቅዱንና የድርጊት መርሃ ግብሩን ይፋ እንደሚያደርግ፣ ለዚሁም ተግባራዊነት ኮንፍራንስ እንደሚያዘጋጅ አመልክተዋል።

በነጻ አውጪ ስም መደራጀትና መታገል ሙሉውን አካል /አገር/ ሊያድን እንደማይችል ያመለከቱት አቶ ኦባንግ “አሁን ትግሬ፣ ኦሮሞ፣ አማራ፣ ጉራጌ፣ ወላይታ፣ ከንባታ፣ ሲዳማ፣ ከፊቾ … እያልን በተበጣጠሰ አመለካከት ከማነከስ የአገራችንን ህልውና በአንድ ትልቅ አጀንዳ ውስጥ በማካተት ለመስራት ድርጅታችን ለሚያቀርበው ጥሪ ህዝብና ጥሪ የሚደረግላቸው ወገኖች ሁሉ ቀና ምላሽ ሊሰጡ ይገባል” ሲሉ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።

ሙስሊም፣ ኦርቶዶክስ፣ ካቶሊክ፣ ፕሮቴስታንት፣ ወዘተ በማለት ከብሄርና ጎሳው ልዩነት በተጨማሪ መለያየት መፈጠሩ የአገሪቱን እጣ ፈንታ አሳዛኝና አደጋ እንኳ ቢፈጠር ለተግሳጽ የሚፈራ ሰው እንዳይኖር ማድረጉ አሳሳቢ የሆነባቸው በርካታ ዜጎች አሉ። አቶ ኦባንግ እንደሚሉት ግን ሁሉም ቦታ የፖለቲካ ኮተት የሌለባቸው፣ ንጹህ ልብና ያላቸውና ህሊናቸውን የሚያከብሩ አሉ። እነዚህ ወገኖች ብቸኛ አማራጭ በሆነው እርቅ ላይ አበክረው መስራት እንደሚገባቸው አመልክተዋል። እሳቸው የሚመሩት አኢጋንም ለእንደዚህ አይነቶቹ ንጹሃን በሩ ክፍት መሆኑን አረጋግጠዋል።

በመጨረሻም “አሁን ችግር በተባባሰባቸው ቦታዎች ሁሉ ‘እርቅ’ እንደ መፍትሄ የሚቀርበው፣ ዓለም አሁን ከመቻቻል ሌላ አማራጭ ስለሌላት ስለሆነ እኛም እርቅ ላይ ያለአንዳች ማቅማማት መስራት ይገባናል፤ ይህ ዕርቅ ግን በደፈናው ምህረት የሚያሰጥ ሳይሆን በፍትህ ላይ የተመሠረተ ነው” ያሉት አቶ ኦባንግ “ድርጅታችን እርቅ ላይ ያለው ሃሳብ ከሌሎች በተለየ የተቋቋምንበት፣ የሰፋና የተፈጠርንበት መሰረት በመሆኑ ይህንን ሃላፊነት በመውሰድ እስካሁን የሰራናቸውን ስራዎች ውጤት ለህዝብ ይፋ እናደርጋለን፤ ይህም እንደወቅቱ ሁኔታ ተለዋዋጭ ሳይሆን የጋራ ንቅናቄው ገና ከጅምሩ የወጠነውና እስካሁን ለዓመታት ሲሰራበት የቆየ ጉዳይ ነው። ኢህአዴግም ሰላም ስለሚያስፈልገው፣ ባለስልጣኖቹም መኖር ስለሚፈልጉ፣ ደጋፊዎቹም ዋስትና ስለሚያሻቸው የተቃዋሚ ወገኖችም አገራቸውን ስለሚያስቀድሙ፣ ሁሉም ወገኖች ቀና ምላሽ ይሰጣሉ ብለን እናምናለን” የሚል መልዕክት አስተላልፈዋል።


ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

የቁጫ ሕዝብ ጥያቄ ሕጋዊ ምላሽ እንዲያገኝ ጥሪ እናቀርባለን!!! አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ (አንድነት)

$
0
0

ከአንድነት ለዴሞክራሲና ፍትህ ፓርቲ (አንድት) የተሰጠ ጋዜጣዊ መግለጫ 

 

ፓርቲያችን አንድነት ከተቋቋመበት ጊዜ ጀምሮ ተግባራዊ እንዲሆኑ ከሚታገልላቸውና ገዥው ፓርቲ ከወረቀት በዘለለ ያልተገበራቸው ሀገራዊ ቁምነገሮች ውስጥ ዜጎች ሳይሸማቀቁ በነፃነት ሃሳባቸውን የመግለፅ፣ በነጻነት የመደራጀት፣ በገዛ ሀገራቸው በነጻነት የመንቀሳቀስ፣ በፈለጉበት አከባቢ የመኖር፣ ሀሳባቸውንና አመለካከታቸውን በነጻነት የመግለጽ፣ የመደገፍ፣ የመቃወም፣ ስለመብታቸው ሳይሸማቀቁ የመጠየቅ ወ.ዘ.ተ እና በአጠቃላይ የሕግ በላይነት እንዲሰፍን፣ የሰብዓዊና ፖለቲካዊ መብቶች በኢትዮጵያ እንዲከበሩ፤ ከዚህም ዜጎች ተጠቃሚ እንዲሆኑ የዜጎች ዋስትና እንዲረጋገጥ ማድረግ ናቸው፡፡

የቁጫ ሕዝብም ያነሷቸውን የማንነት፣ የቋንቋ፣ የባህልና የአስተዳደር ጥያቄዎችን በሠላማዊ መንገድ፣ ዴሞክራሲያዊ መብታቸውን ተጠቅመው ለመንግሥት ቢያቀርቡም የተሰጣቸው ምላሽ እስርና ማስፈራሪያ መሆኑ ፓርቲያችንን አሳዝኖታል፡፡ ግንቦት 28 ቀን 2005 ዓ.ም ጀምሮ በደቡብ ክልል ጋሞ ጎፋ ዞን በቁጫ ወረዳ የሆነውም የዜጎችን ህጋዊ ጥያቄ በሕገ-ወጥነት መቀልበስ መሆኑን መካድ አይቻልም፡፡ መገለጫውም በጅምላ የታሰሩትና እስር ላይ የሚገኙት ዜጎች ናቸው፡፡ ፓርቲያችን ጉዳዩን በቅርበት ተከታትሎ እንዳጣራው በርካቶች በጅምላ የታሰሩበት ምክንያት ልጆቻችን አፋቸውን በፈቱበት ቋንቋ ይማሩ፣ በስማችን ልንጠራ ይገባናል፣ የማንነት ጥያቄያችን ምላሽ ያግኝ፣ ፍህና መልካም አስተዳደር ይረጋገጥ፣ የልማት ጥያቄያችን ምላሽ ያግኝ የሚሉት ዋና ዋናዎቹ ናቸው፡፡ ስርዓቱ አረጋግጫቸዋለሁ ከሚላቸውና በቁጥጥር ስር ባደረጋቸው ሚዲያዎቹ የሚለፍፋቸው ቢሆኑም ለቁጫዎች የተሰጣቸው ምላሽ ሰብዓዊ ክብራቸውን መጣስና ማሰር ነው፡፡ ፓርቲያችን ይህንን ሕገ-ወጥ ተግባር አጥብቆ ይቃወማል፡፡

መንግስትም የመብትና ማንነት ጥያቄ ስላነሱ ያሰራቸውን በአስቸኳይ እንዲፈታ፤ ያነሷቸውን ጥያቄዎች አግባብ ባለው መንገድ በፍጥነት እንዲመልስ እንጠይቃለን፡፡

አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ
ሐምሌ 24 ቀን 2005 ዓ.ም
አዲስ አባባUDJ

Viewing all 15006 articles
Browse latest View live