Quantcast
Channel: Ethiopian News | ዘ-ሐበሻ | Latest News Provider | News For All
Viewing all 15006 articles
Browse latest View live

Sport: ሰር አሌክስ ፈርጉሰን ጡረታ የወጡት ለሚስታቸው ሲሉ መሆኑን ይፋ አደረጉ

$
0
0

Alex Fergusen

አሰልጣኝ ሰር አሌክስ ፈርጉሰን በ2013 ራሳቸውን ከአሰልጣኝነት ሲያገልሉ ማን ያልደነገጠ ነበር? በኦልድትራፎርድ ደግሞ ይሄ ስሜት ፍፁም የተለየ ነበር፡፡ በማንችስተር ዩናይትድ ብቻ ሳይሆን በመላው እንግሊዝ እንደ ፈርጉሰን አይነት ውጤታማ አሰልጣኝ ፈልጎ ማግኘት አይቻልም፡፡
ሰር አሌክስ ጡረታ የመውጣት እቅድም ሆነ ፍላጎት አልነበራቸውም፡፡ ሆኖም የባለቤታቸው ካቲ መንትያ እህት -ብሪጌት ሮበርትሰን ህልፈተ ህይወት ይሄንን ውሳኔ እንዲያሳልፉ እንዳስገደዳቸው ጠቅሰዋል፡፡

‹‹ያለጥርጥር በሥራዬ እቀጥል ነበር›› ብለዋል- ታላቁ አሰልጣን ከቴሌግራፍ ጋዜጣ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ ‹‹በአንድ ምሽት ባለቤቴ (ካቲ ፈርጉሰን) ቴሌቪዝን እየተመለከተች ፊቷ ላይ ጥሩ ነገር አላስተዋልኩም፣ ከቴሌቪዥኑ ይልቅ የቤቱን ጣሪያ ስትመለከት አስተዋልኩኝ፣ የብቸኝነት ስሜት እንደተሰማት አውቃለሁኝ፣ እርሷ እና ብሪጌት መንትያ ነበሩ›› ብለዋል፡፡

የፈርጊ ባለቤት ካቲ አሰልጣኙ ከኃላፊነታቸው እንዲነሱ ጥያቄ ያቀረቡላቸው በ2002 ነበር፡፡ በወቅቱ ታላቁ አሰልጣኝም ይሄንን ውሳኔ ለማሳለፍ ከውሳኔ ላይ ደርሰው እንደነበር ተናግረዋል፡፡ የኋላ ኋላ ውሳኔያቸውን ለውጠው በሚወዱት ሙያ ቀጠሉ እንጂ፡፡

‹‹ለሁለተኛ ጊዜ ይሄንን ጥያቄ ስታነሳልኝ ጥያቄውን ውድቅ ማድረግ አልቻልኩም፤ ከእውነተኛው ምክንያት ውጭ ሌላ ምክንያት ሊኖራት እንደማይችል አውቃለሁኝ›› የሚል አስተያት ሰጥተው በውሳኔያቸውን እንደማይፀፀቱ ገልፀዋል፡፡

የብሪጌት ህይወት ያለፈው በኦክቶበር 2012 ነበር፤ ፈርጊ የባለቤታቸው ስሜት ከመጥፎው አጋጣሚ በኋላ በጎ እንዳልሆነ ተገንዝበዋል፡፡ የአሁኑ ባለቤታቸውን ያገኙት በ1966 በግላስኮው ‹‹የአድማ ስብሰባ›› ላይ ነበር፡፡
ታላቁ አሰልጣኝ የግል ህይወታቸውን የሚተርከው መጽሐፍ ላይ በሰጡት አስተያየት ‹‹ባለቤቴ ሁልጊዜም ቢሆን የቤቱን በር ክፍት አድርጋ ትጠብቀኝ ነበር፤ ሌሊት 8፡00 እና 9፡00 ሰዓት ቤት ስመጣ እንኳን በር ስር ሆና ትጠብቀኝ እንደነበር መናገር አለብኝ፤ ስመጣ የሞቀ አቀባበል ታደርግልኝ ነበር›› ብለዋል፡፡
ፈርጊ ለመጨረሻ ጊዜ ለንባብ ያበቁትን መጽሐፍ ማስታወሻነቱን ለባለቤታቸው መንትያ እህት ብሪጌት አበርክተዋል፡፡ በአሰልጣኝነት ህይወታቸው ስኬታማ የሆኑት በባለቤታቸው ድጋፍ እንደሆነ ለመግለፅ ፍርሃት አልተሰማቸውም፤ ኧረ እንዲያውም ‹‹ቀዳሚዋ እርሷ ናት›› ለማለት አልሰነፉም፡፡
በ39 ዓመት የአሰልጣኝነት ቆይታቸው ላስመዘገቡት ስኬት ባለቤታቸውን ቀዳሚ ሲያደርጉ ብዙዎች ውስጣቸው ተነክቷል፤ ጥሩ ትምህርት እንዳገኙም ጥርጥር የለውም፤ አሰልጣኙ የስኬት እና በአንድ ክለብ ውስጥ ረጅም ዓመት የማሰልጠን ምልክት ናቸው፡፡
እርሳቸው በሜይ 2013 ለ13ኛ ጊዜ የፕሪሚየር ሊጉ ሻምፒዮን ከሆኑ በኋላ የተሾሙት አሰልጣኞችም ቢሆኑ ከስኬት ጋር ተራርቀዋል፡፡ ከሳምንታት በፊት የኔቪል ወንድማማቾች ወላጅ አባት ከዚህ ዓለም በሞት ሲለዩ በቀብር ስነ ስርዓቱ ላይ የተገኙት ፈርጊ በስፍራው ደርሰው ከመኪናቸው ሲወርዱ እዚያ የነበሩ ደጋፊዎች በጣም በጩኸት ስሜት ውስጥ ሆነው ‹‹እናመሰግናለን፤ ሰር አሌክስ›› ብለዋቸዋል፡፡
በማንችስተር ዩናይትድ የነበራቸውን የ26 ዓመት ቆይታ አስመልክተው ‹‹ጡረታ እንደምወጣ እያወቅኩኝ እንኳን የክለቡን ደረጃ ለማስጠበቅ ጥረት ሳደርግ ነበር፤ ደካማ በሚባሉ ቦታዎች ላይ ተጨዋቾችን ማስፈረም ነበረብን፤ በምንም ነገር ዙሪያ ስለማንችስተር ዩናይትድ ስናገር የአውቶብሱ ጉዞ እንደሚቀጥል ገልጫለሁኝ፣ ማንም ወደ ኋላ አይቀርም፤ በቀጣይ መዳረሻችንን በተመለከተ ሁሉም አካል በእኛ ላይ ሙሉ እምነት ነበረው›› የሚል አስተያየትን ሰጥተዋል- ፈርጊ፡፡
Alex-Ferguson
ህይወት ከኦልድ ትራፎርድ በኋላ
ፈርጉሰን ውሳኔያቸውን ካሳለፉ በኋላ ወደ ኋላ አልተመለሱም፣ ውሳኔያቸውን ተከትሎ ቀጣይ ስራቸውን የወሰኑት ቀደም ብለው ነበር፡፡
‹‹ጡረታ ከወጣሁኝ በኋላ ዕድሜው እንደገፋ ሰው ያለ ሥራ መቀመጥን አልመረጥኩም›› ይላሉ- ቁጡው አሰልጣኝ፡፡
ጨምረውም ‹‹አባቴ ከመርከብ ሥራው ጡረታ የወጣው በ65 ዓመቱ ነበር፤ በግሌ እርሱ እንደሆነው መቀመጥን አልመረጠም፣ በሃርቫርድ ዩኒቨርሲቲ (በትርፍ ጊዜያቸው በሃርቫርድ ቢዝነስ ስኩል ያስተምራሉ) መስራት ነበረብኝ፡፡…
…ከዚያ ውጭ በዩናይትድ እንደ ዳይሬክተር እና አምባሳደር እንዲሁም ከአውሮፓ እግር ኳስ ማህበር እና (ዩኒሴፍ) ጋር መስራትን መርጫለሁኝ፤ ከዩናይትድ ጋር በየዓለማቱ በመጓዝ ቡድኑ ሲጫወት መመልከት ያስደስተኛል›› ሲሉ አስረድተዋል፡፡

የፈርጉሰን ስኬት ምስጢር
የዘመኑ እግርኳስ እንደ ሰር አሌክስ አይነት ስኬታማ አሰልጣኝ ተመልክቶ አያውቅም፤ ፈርጊ ሁልጊዜም አንድን አሰልጣን ለስኬት የሚያበቃው ‹‹ስብዕናው፣ በውስጡ ያለው ኃይል፣ ውሳኔ ሰጪነቱ (የውሳኔ ሰው መሆን)፣ አስተውሎቱ እና ግንኙነቱ ነው›› የሚል መረጃን ሰጥተው ‹‹ይህ በኬብል ካምፓኒ አልያም ባርክሌይስ ባንክ ለሚሰራ ሰው ሳይቀር ይሰራል፣ ሁልጊዜም ቢሆን የምትገናኘው ከሰው ልጅ ጋር ነው፣ ከሰው ልጅ ጋር ስትገናኝ ደግሞ ቀጥተኛ መሆን እና ተነሳሽነት መፍጠር ግድ ይልሃል፣ በአለቃቸው ላይ ከፍተኛ እምነት ሊኖራቸው ይገባል›› በማለት ምስክርነታቸውን ገልፀዋል፡፡
ፈርጊ በመጽሐፋቸው ላይ የስኬታማነታቸውን ምስጢር በግልፅ ዘርዝረዋል፣ ወደ ኋላ መለስ ብለውም ‹‹ምንም ነገር ለማድረግ አልፈራም ነበር፤ ተጋጣሚዬን ለማሸነፍ ምንም አይነት ሪስክ ከመውሰድ ወደኋላ አልልም፤ ከዚህ በተጨማሪም በወጣት ተጨዋቾች መጠቀም ያስደስተኛል›› የሚል አስተያየትን ሰጥተው ‹‹በወጣበት ተጨዋቾች ላይ ከፍተኛ እምነት አለኝ፤ በአበርዲንም ሆነ ሴይንት ሜሪን ወጣት ተጨዋቾችን ለታላቅ ስኬት የማብቃት ችግር አልነበረብኝም፤ ወደ ማንቸስተር ዩናይትድ ከመጣሁኝ በኋላ በ1950ዎቹ ሰር ማት በስፒ የሰራውን ነገር መድገም ነበረብኝ፣ ማንቸስተር ዩናይትድ እና ወጣት ተጨዋቾች የአንድ ሣንቲም ሁለት ገጽታ ናቸው፡፡ ይሄ እውነታ ለግማሽ ምዕተ ዓመት በኦልድ ትራፎርድ ሲተገበር ነበር›› በማለት የክለቡን ባህል ለማስቀጠል ባደረጉት ጥረት እንደሚኮሩ ገልፀዋል፡፡
ማንችስተር ዩናይትድ ለሁለት አስርት ዓመታት በባለግርማ ሞገሱ አሰልጣን ተመርቷል፤ በጎቫን በአስቸጋሪ ውጣ ውረድ ያለፉት ፈርጊ ወደ ማንችስተር ዩናይትድ ከመምጣታቸው በፊት በስኮትላንድ በተጨዋችነት እና አሰልጣንነት አገልግለዋል፡፡ በተጨዋችነት ዘመናቸው ኃይል እና ጉልበትን ቀላቅለው የተጋጣሚ ቡድን ተከላካዮችን ስቃይ ውስጥ ይከትቱ ነበር፤ በአሰልጣንነት ዘመናቸው ደግሞ ቁጡነታቸው የሚዘነጋ አይደለም፡፡
‹‹የመጣህበት መንገድ ለአለሰልጣኝነት ህይወቴ ጠቅሞኛል፤ ጥቂት እድለ ቢስ የሆኑ ሰዎችን ስናግዝ ቆይተናል፡፡ ለምሳሌ በጀማሪ ሰራተኞች አድማ ላይ መሳተፍ አያስፈልገኝም፣ አልያም እነኚህ ጀማሪ ሰራተኞች በአድማ ላይ ተሳታፊ እንዲሆኑ ማበረታታት አይጠበቅብኝም፡፡ እኛ (የፋብሪካ ሠራተኞች) ጥሩ ክፍያ ይከፈለን ነበር፤ ችግር አልነበረብንም›› የሚል አስተያየትን ሰጥተው ‹‹የአሰልጣኝነት ፍቃድ ያገኘሁት በ24 ዓመቴ ነበር፡፡ ዕድሜዬ 32 ሲሞላ ለአሰልጣኝነት ዝግጁ ነበርኩኝ፤ እየተጫወትኩኝ አሰለጥን ስለነበር ለመወሰን አልቸገርኩም፡፡ በእግር ኳሱ ኢንዱስትሪ መማር አለብህ፣ አለበለዚያ በስራው መቆየት አትችልም›› በማለት አሰልጣኝነት ፈታኝ ሙያ እንደሆነ ገልፀዋል፡፡
በቁጣ ተጨዋቾችን የሚያርዱት ታላቁ አሰልጣኝ በግላስኮው ቡና ቤት ከፍተው ይሰሩ ነበር፡፡ ወደኋላ ተመልሰው ‹‹ቡና ቤት አስቸጋሪ ስራ ነው፣ ይሰለቻል፣ ቅዳሜ ማታ ያለው ግርግር ይፈትናል፣ ሰዎች ይወጣሉ- ይገባሉ፡፡ የአሰልጣኝነት ዕድል ሳገኝ ስኬታማ መሆን እንደምችል ለራሴ ነገርኩት፣ እርግጥ ነው አሰልጣኝነት የውድቀት ስጋት አብሮ ያስከትላል፣ ነገር ግን ወደ ቡና ቤት ከመመለስ በአሰልጣኝነት ሙያ ስኬታማ መሆን እንዳለብኝ ቁርጠኛ ሆንኩኝ፣ በጭራሽ ወደኋላ ማሰብ እና መመለስ አላስፈለገኝም›› የሚል መረጃን ይሰጣሉ፡፡
በመጀመሪያ ክለባቸው ፈርጊ ተቸግረው ነበር፤ ያገኙት ባጀት እና የተጨዋቾች ቁጥር አነስተኛ መሆን አሰልጣኙን ፈትኗቸዋል፡፡
‹‹በአበርዲን በጣም ብዙ ነገሮችን ተምሬያለሁኝ፤ በመልበሻ ክፍል ውስጥ ጠንካራ ማንነት ይዞ መቅረብ እና በወጣት ተጨዋቾች ላይ መሥራት አስፈላጊ እንደሆነ ተገነዘብኩኝ›› የሚል አስተያየትን የሚሰጡት ፈርጉሰን በማንችስተር ዩናይትድ ተመሳሳይ የሆነ አካሄድን ተጉዘው እንደ ብሪያን ሮብሰን፣ ብሪያን ማክሌር፣ ማርክ ሂዩስ፣ ስቲቭ ብሩስ፣ ፖል ኢንስ እና ሮይ ኪንን የመሳሰሉ ተጨዋቾች ከታች አንስተው ለታላቅነት ለማብቃት አልተቸገሩም፡፡
ግልፅ የሆነ የመሪነት መርህ ያላቸው ቁርጠኛው አሰልጣኝ ‹‹ተጨዋቾቹ የማይደሰቱበትን ነገር በጠንካራ ማንነት መለወጥ ይቻላል፤ የዚህ አይነት ሰብዕና የተጨዋቾችን ማንነት ይለውጣል፤ ቁርጠኛ እንዲሆኑ ያደርጋል፡፡ የአሸናፊነት መንፈስ ያሰርፃል፣ በቃ ነገሩ ይህን ያህል ቀላል ነው›› የሚል አስተያየትን ይሰጣሉ፡፡
እርግጥ ነው ከሰራተኛው መደብ መገኘታቸው በስልጠናው ውጤታማ እንዲሆኑ አስችሏቸዋል፤ ‹‹ከንጋቱ 11፡00 እና 12፡00 ላይ ከእንቅልፋቸው ተነስተው የማሽን ስራዎች ላይ የሚጠመዱ ሰዎችን መመልከት ለስራ ያነሳሳል፣ ሥራዎች የሚሰሩት በጋራ በመሆኑ የራሱ የሆነ ተፅዕኖ ይኖረዋል›› ይላሉ፡፡

የመጨረሻዎቹ ዓመታት ፈተና
ሰር አሌክስ ጡረታ ከመውጣታቸው በፊት የነበሩት የመጨረሻዎቹ ዓመታት ከተለያዩ ስመጥር ተጨዋቾች ጋር መጋፈጥ ነበረባቸው፤ ዴቪድ ቤካም በማንቸስተር ዩናይትድ የስኬት ዘመን ቁልፍ ከሚባሉ ተጨዋቾች መሀከል አንዱ ቢሆንም የኋላ ኋላ በሁለቱ ግለሰቦች መሀከል አለመግባባት ተፈጥሮ እንግሊዛዊው ለስንብት ተዳርጓል፡፡ አሰልጣኙ በ2003 ወደ ሪያል ማድሪድ እንዲያመራ ቢያደርጉም አሁን ግን ሁሉም ነገር አልፎ በድጋሚ ወዳጅነት መስርተዋል፡፡
‹‹ነገሮችን መቆጣጠር ያስፈልጋል፤ ለራስ የሚራ ከፍ ያለ ዓት መቆጣጠር አያስቸግረኝም፤ (ክርስቲያኖ) ሮናልዶ ከመስታወት ፊት ቆሞ ሊቀነጃጅ ይችላል፡፡ ይህንን የምመለከተው በበጎ ስሜት ነው፡፡ የተጋጣሚ ቡድን ተጨዋቾች እርሱን ለማቆም የመሰላቸውን ጥፋት ሊፈፅሙ ይችላሉ›› ይላሉ፡፡
‹‹አንድ ተጨዋች ፌራሪ መኪና እየነዳ ለምን ይሄንን የመኪና ሞዴል እንደመረጠ ራሳችሁን ለትጠይቁ ትችላላችሁ፤ ሆኖም ይህ የእርሱ ምርጫ ነው፡፡ በሊጉ መጨረሻ ወይም በወረደ ክለብ ውስጥ የሚገኝ ተጨዋች ያንን መኪና ይዞ ከተማ ውስጥ ሊያሽከረክር አይችልም፡፡ አንዳንድ ሰዎች ይህንን መተግበር ይከብዳቸዋል፣ እውነተኛ ተጨዋቾች በዚህ ረገድ አይቸገሩም››
ኤሪክ ካንቶናን ተቆጣጥሮ ለስኬት መብቃት የቻለ አሰልጣኝ ምንም ነገር የሚሳነው አይመስልም፣ ‹‹ከካንቶና ጋር በየዕለቱ አወራ ነበር፤ የሚገባውን ክብር ያላገኘ መሳጭ ሰው ነው፣ በትክክለኛ ክለብ ውስጥ ስለነበር የሚፈልገው የሚያበረታታው ሰው ነበር፤ በልምምድ ሜዳ ላይ ተዳክሞ እና ዓይኑ ጠብቦ ልትመለከቱት ትችላላችሁ፣ የድብርት ስሜት ተጫጭኖት ምንድነው የሆነው? እንድትሉ ያደርጋል፡፡ ሆኖም አንድ ጊዜ ልምምድ ከጀመረ በኋላ ሁሉም ነገር ያስተካክላል›› የሚል መረጃን ሰጥተው ‹‹ሮናልዶ ሌላው ታላቅ ተጨዋች ነበር፣ ግን ደግሞ ፍፁም ፕሮፌሽናል እግር ኳስ ተጨዋች ነው፣ ሁሉንም ነገር በአግባቡ ይፈፅማል›› በማለት ከትልልቅ ተጨዋቾች ጋር በምን አይነት ሁኔታ ውስጥ አልፈው እንደሰሩ ይናገራሉ፡፡
በአሰልጣኝነት ዓለም የፈርጉሰን ቀዳሚ መርህ ሌሎችን ማመን ነው፡፡ ነገሩ በሁለቱም መንገድ ይገለፃል፤ ይህንን መርህ እንዲያብራሩ ጥያቄ ስታቀርቡላቸው ‹‹በአሰልጣኝነት ቁልፉ ነገር በተጨዋቾቹ ላይ ከፍ ያለ እምነት መጣል ነው፡፡ እምነት ስትጥል ምንም ነገር ፈልገህ ሊሆን አይገባም፤ ለአንተ በመጫወታቸው የምቾት ስሜት እንዲሰማቸው ማድረግ ግድ ነው፡፡ ራስህን ለእነርሱ አሳልፈህ መስጠት አለብህ፤ ሁልጊዜም ቢሆን ‹‹ይኸውላችሁ፤ እዚህ የተገኘሁት በአንድ ምክንያት ነው፡፡ ያላችሁን ምርጥ ብቃት አውጥታችሁ እንድትጠቀሙ እሻለሁኝ፣ ይህ ምርጥ ሰው እንድትሆኑ ያስችላችኋል፤ በዚህ ላይ ጥሩ ክፍያ ታገኛላችሁ እላቸዋለሁኝ፣ በማንቸስተር ዩናይትድ ይህንን ስፈፅም ነበር፡፡ ተጨዋቾቹ የራሴ ናቸው፣ ስኬታማ እንድሆን አግዘውኛል፣ ስለዚህ ለእነርሱ ታማኝ መሆን ነበረብኝ›› የሚል ምላሽ ይሰጣሉ፡፡

‹‹ፀጉር አድርቅ›› ቁጣ
የፈርጉሰን ቁጣ አስፈሪ ነው፡፡ ኧረ እንዲያውም የሚያስበረግግ በመሆኑ ‹‹ፀጉር አድርቅ›› ቁጣ እስከመባል ደርሷል፤ ‹‹ይሄ የማይረባ ስም ለረጅም ዓመታት አብሮኝ ኖሯል፣ ሆኖም ቡድኔ በጭራሽ በፍርሃት ስሜት ተሸብቦ አልተጫወተም፣ አንድ ተጨዋች እንኳን በዚህ ስሜት ውስጥ ሆኖ አልተጫወተም፡፡ ተጨዋቾቼ በሙሉ ያላቸውን አቅም አውጥተው ሲጫወቱ ቆይተዋል፣ ሁልጊዜም ቢሆን ጀብደኛ ነበሩ፤ በቃ መልሱ ይኸው ነው›› ይላሉ፡፡
‹‹እርግጥ ነው በትክክለኛ ምክንያት ስሜትን መቆጣጠር አለመቻል ወይም መበሳጨት ክለቡ ማንችስተር ዩናይትድ እንደሆነ መታወቅ አለበት፤ ይሄ ነገር ካልረዳነው ትርጉሙ አይገባንም፡፡
‹‹አንድ አባባል አለን፤ ማንም በርህን አንኳኩቶ ገንዘብ አይሰጥህም፡፡ በሩን አንኳኩተህ አንድ የሆነ ነገር ማግኘት ያስፈልጋል፡፡ ወደ ሜዳ ውስጥ ገብተህ ጨዋታውን በማሸነፍ ገንዘብ ማግኘት አለብህ››
ሰር አሌክስ ተጨዋቾቻቸውን ለተደራራቢ ስኬት ያበቁበት የራሳቸው አካሄድ አላቸው፡፡ ‹‹ብዙዎቹን ምን ያህል ሜዳልያ አንገታቸው ላይ እንዲጠብቁ እጠይቃቸዋለሁኝ፤ (ራያን) ጊግስ ላይ ደርሳችኋል? የሚል ጥያቄ አነሳላቸዋለሁኝ፤ ስንቶቻችሁ ዘጠኝ ጊዜ አሳክታችኋል? ለ10ኛ ጊዜ ይህንን ክብር ማግኘት አትፈልጉም? እላቸዋለሁኝ›› ይላሉ፡፡
ከፈርጉሰን ስኬት በርካታ ነገሮች መማር ይቻላል፤ ጡረታ መውጣት ከክለብ ባለቤቶች፣ ሊቀመንበሮች እና ስራ አስኪያጆች ጋር በምን አይነት መልኩ ‹‹ንግግር ማድረግ›› እንዳለባቸው እንደተረዱ የገለፁት አሰልጣኝ ‹‹ዓለምን መቆጣጠር እችላለሁኝ›› የሚል አስተሳሰብ ጤናማ አይደለም፡፡ ከሜዳ ላይ ሰራተኞች እንዲሁም ከፅዳት እና ሻይ ቤት ሰራተኞች ጋር መነጋገር ተገቢ ነው›› የሚል አስተያየትን ይሰጣሉ፡፡
በስፒ፣ ጃክ ስቴይን እና ቢል ሻንክሌ ስኬታማ አሰልጣን ነበሩ፤ ‹‹ንግግርህ ግልፅ መሆን አለበት፤ ትክክለኛውን መረጃ ለተጨዋቾቹ በማስተላለፍ የምትፈልገውን ነገር ማግኘት ይቻላል›› ይሄ የፈርጊ የመጨረሻ ቃል ነው፡፡

The post Sport: ሰር አሌክስ ፈርጉሰን ጡረታ የወጡት ለሚስታቸው ሲሉ መሆኑን ይፋ አደረጉ appeared first on Zehabesha Amharic.


Health: እርግዝናና የስኳር በሽታ (ከህክምና ባለሙያ ጋር የተደረገ ቃለምልልስ)

$
0
0
Pregnant woman, mid section

Pregnant woman, mid section

በበርካታ ጤና ነክ የጥናት ጽሑፎች ላይ እንደተመለከተው፣ በአንድ ሰው ደም ውስጥ በአማካኝ ከ70 እስከ 105 ሚሊ ግራም በዲሲ ሌትር ስኳር ካለ ትክክለኛ (መደበኛ) ተብሎ ይወሰዳል፡፡ በአንፃሩ ደግሞ ከ126 ሚሊ ግራም በዲሲ ሊትር በላይ ስኳር በደም ውስጥ ከተገኘ ግለሰቡ የስኳር ህመምተኛ ሆኗል ማለት ይቻላል፡፡

እዚህ ላይ በሰውነት ውስጥ የስኳር መጠን ለምን ከፍ ይላል የሚል ጥያቄ መነሳቱ አይቀርም፡፡ ቆሽት የተሰኘው የሰውነታችን ክፍል በአንድም ይሁን በሌላ ምክንያት፣ ኢንሱሊን የማምረቱ ተግባር ሲስተጓጎል በደም ውስጥ ያለ የግሉኮስ (የስኳር) መጠን ከፍ ማለቱ አይቀርም፡፡ ሁላችንም የምንመገበው ምግብ ይነስም ይብዛ በተለያዩ ኬሚካላዊ ለውጦች ወደ ስኳርነት ይለወጣል፡፡ የበላነው ምግብ ወደ አስፈላጊው ስኳርነት ከተወለጠ በኋላ፣ በሰውነታችን ውስጥ ገብቶ የሚጠበቅበት ተግባር እንዲከናወን ኢንሱሊን በምንም የማይተካ ሚና ይኖረዋል፡፡
ኢንሱሊን ስኳርን ጨምሮ ሌሎች እጅግ አስፈላጊ የሆኑ ነጥረ ነገሮች በህዋሳቶች አማካኝነት ወደተቀረው የሰውነት ክፍላችን እንዲደርስ ያደርጋል፡፡
ቆሽት የተባለው የሰውነት ክፍላችን፣ የኢንሱሊን ሆርሞንን በከፊል ወይም ሙሉ በሙሉ በሚባል ደረጃ ማመንጨት (ማምረት) ሊያቆም ይችላል፡፡ ወይም ደግሞ የሚመነጨው ኢንሱሊን ሰውነታችን የሚፈለገውን መጠን ያህል አይሆንም ይሆናል፡፡ አልያም የመነጨው ኢንሱሊን የመጠን ችግር ባይኖርበትም በተገቢው መንገድ ዕለታዊ ተግባሩን ማከናወን ሳይችል የሚቀርበት ሁኔታ አለ፡፡ በእነዚህ ምክንያቶች የበላነው ምግብ ሂደቱን ጠብቆ ወደ ስኳርነት ከተለወጠ በኋላ ህዋሶቻችን ውስጥ ገብቶ ጥቅም መስጠት ሲገባው፣ ያለምንም ተግባር በደም ውስጥ ይከማቻል፡፡ በዚህ ወቅት ነው እንግዲህ ስኳር በደም ውስጥ ከተገቢው መጠን በላይ ከፍ ብሏል አልያም የስኳር በሽታ ተከስቷል የሚባለው፡፡
ለስኳር በሽታ መከሰት ተቀዳሚ ምክንያት፣ ከቆሽት ተግባር መስተጓጎል (መጎዳት) ጋር የጠበቀ ትስስር ያለው ነው፡፡ ለመሆኑ የስኳር በሽታ አጋላጭ ምክንያቶች ምንድናቸው? ከእርግዝና ጋር በተያያዘ የሚከሰተው የስኳር በሽታ የትኛው ዓይነት ነው? ለምን እርግዝናን ጠብቆ ይከሰታል? መፍትሄውስ ምንድን ነው? ለእነዚህና ተያያዥ ጉዳዮች ሙያዊ ማብራሪያ እንዲሰጡን አንድ የህክምና ባለሙያን አነጋግረናል፡፡ መልካም ንባብ!

ጥያቄ፡- ለስኳር ህመም አጋላጭ ምክንያቶች ምንድናቸው ይላሉ?
ዶ/ር፡- ቀደም ሲል በወላጆች ወይም ቅርብ በሚባለው ቤተሰብ ውስጥ የትኛውም አይነት የስኳር ህመም የተከሰተበት አጋጣሚ ከነበረ፣ የሰውነት የክብደት መጠን /Body mass index/ ከጨመረና ከ140 በ90 ከፍ ያለ የደም ግፊት ችግር ካለ፣ ለስኳር በሽታ የመጋለጥ ዕድል ከ80 በመቶ በላይ የሰፋ ይሆናል፡፡ ዕድሜያቸው ከ45 ዓመት በታች የሆኑ ነገር ግን የደም ግፊትና በደም ውስጥ የቅባት መጠን የመጨመር ሁኔታ ካለ፣ በሳምንት 3 ቀን ከአንድ ሰዓት በላይ ለሚሆን ጊዜ አካላዊ እንቅስቃሴ የማይደረግ ከሆነ፣ የዘወትር የአመጋገብ ስርዓት ከጣፋጭ ምግቦች ጋር የጠበቀ ቁርኝት ያለው ከሆነ፣ የካርቦ ሃይድሬትና የቅባት መጠናቸው ከፍ ያሉ ምግቦችን አዘውትሮ የመመገብ ልምድ ካለ፣ ለአንደኛው ዓይነት የስኳር በሽታ ተጋላጭ የመሆንን ዕድል ያሰፋዋል፡፡
በሁሉም እናቶች ላይ ባይባልም፣ በእርግዝና ወቅት የስኳር መጠን የመጨመር ሁኔታ ይከሰታል፡፡ በዚህ ወቅት በስኳር ህመምተኛነት ተፈርጀው የቆዩ ነፍሰጡር እናቶች ከወሊድ በኋላ የስኳር ህመሙ የጠፋላቸው ከሆነ፣ ከ9 ፓውንድ በላይ ክብደት ያለው ልጅ ከወለዱ፣ በሰውነታቸው ውስጥ ከፍተኛ መጠን ያለው የስብ ክምችት ካለ፣ አካላዊ እንቅስቃሴ የማድረግ ልምዱ ከሌላቸው፣ የየዕለት አኗኗራቸው በጭንቀትና ውጥረት የተሞላ ከሆነ፣ ለስኳር በሽታ ተጋላጭ የመሆናቸውመጠን ከፍ ያለ ነው፡፡
ከመሰል ችግሮች በተጨማሪ የልብ፣ የኩላሊት፣ የስትሮክና የመሳሰሉ ስር የሰደዱ የጤና ችግሮች ካሉ፣ በ2ኛው ዓይነት የስኳር በሽታ 97 በመቶ ተጋላጭነትን ያስከትላል፡፡ ሌላውና ለስኳር ህመም አጋላጭ ምክንያት የሆነው የአልኮል ሱሰኛ መሆን ነው፡፡ ሌሎች አነስተኛ ድርሻ ያላቸው አጋላጭ ምክንያቶች እንዳሉ ታሳቢ ቢደረግም፣ ከላይ የዘረዘርናቸው ዋና ዋና ጉዳዮች ለጤና ችግሩ የመጋለጥ አጋጣሚን ከ80 እስከ 90 በመቶ ድረስ የሚያሰፉ ናቸው፡፡ ስለሆነም በዚህ ወቅት ፈጠን ብሎ ሐኪምን በማማከር የደም ውስጥ የግሉኮስ መጠንን ማስለካት ይገባል፡፡

ጥያቄ፡- የስኳር በሽታ አይነቶች ካሉት ቢገልፁልኝ?
ዶ/ር፡- የስኳር ህመም አልፎ አልፎ ወይም በውስን በሆነ ደረጃ የሚከሰቱትን ሳይጨምር በዓለም አቀፍ ደረጃ ትኩረት ያገኙት አራት አይነት ናቸው፡፡ እነሱም አንደኛው አይነት፣ ሁለተኛ አይነት፣ ሶስተኛው አይነት እና አራተኛው ዓይነት የስኳር ህመም በመባል ይታወቃል፡፡
አንደኛው አይነት የስኳር ህመም /Type 1 diabetes/
በአብዛኛው ከ30 ዓመት በታች በሆኑ ወጣቶች፣ ታዳጊ ወጣቶችንና ህፃናት ላይ የሚከሰት ነው፡፡ ይህ አይነቱ የስኳር ህመም የሚከሰተው ቆሽት ሙሉ በሙሉ ኢንሱሊን ማመንጨት (ማምረት) ስታቆም እንደሆነ በዘርፉ የተጠኑ ጥናቶች ያመለክታሉ፡፡ የዓለም ጤና ድርጅት (WHO) እ.ኤ.አ በ2008፣ በ2009 እና በ2010 ያወጣው መረጃ እንደሚያስገነዝበው፣ በዓለም ላይ ከሚገኙ 246 ሚሊዮን የስኳር ህሙማን ውስጥ በአንደኛው አይነት የስኳር ህመም የታመሙ 15 በመቶ ናቸው፡፡ የአንደኛው አይነት የስኳር ህመም ሲከሰት ከሚታዩ ምልክቶች መካከል ቶሎ ቶሎ ውሃ መጥማት፣ ሽንት መብዛት፣ አሁንም አሁንም መራብና የሰውነት ክብደት መቀነስ ዋና ዋና የሚባሉ ናቸው፡፡ ህመሙ በጊዜው ታውቆና ተገቢው ህክምና ካልተደረገለት በስተቀር እስከ ሞት የሚዘልቅ አደጋን ሊያመጣ ይችላል፡፡
ሁለተኛው ዓይነት የስኳር ህመም /Type 2 diabetes/
ይህ አይነቱ የስኳር በሽታ፣ አብዛኛውን ጊዜ ማለት ይቻላል የሚጀምረው ከ40 ዓመት ዕድሜ በኋላ ነው፡፡ አንዳንድ ጊዜ ግን በ30ዎቹ ዕድሜ ውስጥም የመከሰት አጋጣሚ ሊኖረው እንደሚችል መዘንጋት የለበትም፡፡ የችግሩ መንስኤ ቆሽት ኢንሱሊን ማምረት (ማመንጨት) ባያቆምም፣ የሚመነጨው ኢንሱሊን በቂ ባለመሆኑ አልያም የተመረተው ኢንሱሊን በተገቢው መንገድ መስራት ባለመቻሉ ነው፡፡ በሰውነታቸው ውስጥ ከፍተኛ የሆነ የስብ ክምችት ያለባቸውና የሰውነት ክብደታቸው ከBody Mass ኢንዴክሳቸው ጋር የማይመጣጠን ከሆነ፣ ለሁለተኛው ዓይነት የስኳር በሽታ ተጋላጭ የመሆን ዕድል ያላቸው ናቸው፡፡ ለአደጋው ተጋላጭ የሚሆኑት ከላይ የገለጽናቸው እንደተጠበቁ ሆነው፣ የአካል እንቅስቃሴ የማያደርጉ፣ ለአካላዊ ጤናቸው ከሚያስፈልገው በላይ የስብ፣ የካርቦሃይድሬት መጠን ያላቸውና አሰር (ገለባ) የሌላቸውን ምግቦች የሚያዘወትሩ ሰዎች ለችግሩ ይበልጥ ተጋላጭ ናቸው፡፡
በሁለተኛው ዓይነት የስኳር ህመም የተያዙ ሰዎች ሁሉ ተመሳሳይ ምልክት አያሳዩም፡፡ ጭራሹንም ለሌላ በሽታ ምርመራ ለማድረግ ሄደው፣ በአጋጣሚ እስካላወቁት ድረስ በሽታው ምንም አይነት ምልክት ላያሳይ ይችላል፡፡ በአብዛኛው ግን ቀደም ሲል ለአንደኛው የስኳር በሽታ፣ ከሁለተኛው ዓይነት የስኳር ህመም ጋር የሚኖሩ ሰዎች፣ በዓለም ላይ ካሉ የስኳር ህሙማን መካከል ከ85 እስከ 90 በመቶ የሚደርስ ድርሻ ይኖረዋል፡፡
ሶስተኛው ዓይነት የስኳር ህመም /Type 3 diabetes/
ይህ አይነቱ የስኳር በሽታ፣ ዘወትሮአዊ (የተለምዶ) ሳይሆን አልፎ አልፎ የሚከሰት ነው፡፡ ብዙ ጊዜ ማለት ይቻላል ከሌሎች በሽታዎች ጋር በተጓዳኝ የሚመጣ በሽታ ነው፡፡
አራተኛ ዓይነት የስኳር ህመም /gestational diabetes/
አንዲት እናት ከእርግዝና በፊት ምንም አይነት የስኳር በሽታ ሳይኖርባት፣ በመጀመሪያው የእርግዝና ጊዜዎች የሚከሰት በሽታ ነው፡፡ ነገር ግ ከወሊድ በኋላ በአሉት 6 ሳምንታት ጨርሶ ሊጠፋ ይችላል፡፡ በዓለም አቀፍ የተጠኑ ጥናቶች እንደሚያሳዩት፣ በዓለም ላይ ካሉ ሴቶች 1 በመቶ የሚሆኑት እርግዝናን ተከትሎ ለሚከሰት ስኳር በሽታ ተጋላጭ ናቸው፡፡ በሀገራችንም ችግሩ በምን ደረጃ ላይ እንዳለ የተጠና ጥናት ባይኖርም የጤና ተቋማትን መሰረት ያደረጉ አንዳንድ ጥናቶች እንደሚያመላክቱት ከሆነ፣ በሀገራችን ያለው ሁኔታም ከዓለም አቀፉ የተለየ አለመሆኑን ነው፡፡ ህመሙ ምንም እንኳን ከወሊድ በኋላ ይጠፋል ቢባልም፣ የኋላ ኋላ ግን መደበኛ የስኳር በሽታ ታማሚ ወደመሆን የመሸጋገር ዕድል ያለ በመሆኑ በየጊዜው የህክምና ክትትል ማድረግ ይጠበቅባቸዋል፡፡

ጥያቄ፡- በእርግዝና ወቅት የሚከሰተው ስኳር በሽታ መንስኤው ምንድን ነው?
ዶ/ር፡- ዋነኛ መንስኤ ተብሎ የሚታመነው፣ በእርግዝና ወቅት ከእንግዴ ልጁ የሚወጡ ሆርሞኖች ናቸው፡፡ በእርግዝና ወቅት እናትየዋ በምግቦች አማካኝነት የምትወስደው የግሉኮስ መጠን ከፍተኛ ከሆነ ወደ ፅንሱ የሚገባው ግሉኮስ መጠንም ከፍተኛ ይሆናል፡፡ በአንፃሩ ደግሞ እናትየዋ በምግብ አማካኝነት የምታገኘው የግሉኮስ መጠን ዝቅተኛ ከሆነ ወደ ፅንሱ የሚደርሰው የግሉኮስ መጠንም ዝቅተኛ ይሆናል፡፡
ይህ እንዳይሆን ተፈጥሯዊ በሆነ መንገድ ከእንግዴ ልጁ በሚመነጩ ሆርሞኖች አማካኝነት፣ ፅንሱ ሁልጊዜም ተመጣጣኝ የምግብ ንጥረ ነገር እንዲያገኝ ይደረጋል፡፡ ነገር ግን እናትየዋ ምግብ ከተመገበች በኋላ በደሟ ውስጥ ግሉኮስ ይፈጠራል፡፡ ሂደቱን ጠብቆም በደም አማካኝነት ወደ ሰውነት ይሰራጫል፡፡ በዚህ ወቅት ወደ ፅንሱ የሚደርሰው ግሉኮስ መጠኑ ዝቅተኛ ይሆናል፡፡ ይሄን ለማስተካከል የእንግዴ ልጁ ሂማን ፕላሴንታ ላፕቶጂን በሚባል ሆርሞን አማካኝነት ወደ እናትየዋ ህዋስ ግሉኮስ እንዳይገባ ያደርጋል፡፡
በዚህም ሳቢያ በእናትየዋ ውስጥ የሚከማቸው የግሉኮስ ከመጠን በላይ ከፍ ይላል፡፡ በመሆኑም እናትየዋ መጠቀም የሚገባት ግሉኮስ ወደ ህዋሳቶቹ ሳይገባ ይቀርና ወደ ፅንሱ እንዲገባ ለማድረግ ሲባል በደም ውስጥ በጣም ብዙ ግሉኮስ ይከማቻል፡፡ በዚህ ጊዜ ጣፊያ የተከማቸውን ግሉኮስ ወደ ደም ውስጥ ለማስገባት ከፍ ያለ መጠን ያለው ኢንሱሊን እንዲመረት ያደርጋል፡፡
ይሁን እንጂ የተከማቸው የግሉኮስ መጠን ወደ ደም ውስጥ አይገባም፡፡ በዚህም ሳቢያ በሰውነት ውስጥ የስኳር መጠን በከፍተኛ ሁኔታ ስለሚጨመር በእርግዝና ወቅት ስኳር በሽታ ይከሰታል፡፡

ጥያቄ፡- በዚህ ችግር ይበልጥ ተጋላጭ የሚሆኑት እነማን ናቸው?
ዶ/ር፡- ከፍተኛ የሰውነት ውፍረት ያላቸው፣ በቤተሰብ ታሪክ ውስጥ የስኳር በሽታ የነበረበት የቤተሰብ አባል ካለ፣ በአልታወቀ ምክንያት ከዚህ በፊት ፅንስ የጠፋባቸው ሴቶች፣ ከዚህ በፊት የአፈጣጠር ችግር ያለበት ልጅ የወለዱ፣ ከ35 ዓመት በላይ የሆናቸውና በተለያዩ ምክንያቶች ዘግይተው የሚወልዱ ሴቶች በእርግዝና ወቅት ለሚከሰት የስኳር በሽታ የበለጠ ተጋላጭ ናቸው፡፡

ጥያቄ፡- ህመሙ ሲከሰት የሚያሳያቸው ምልክቶች የትኞቹ ናቸው?
ዶ/ር፡- መደበኛው የስኳር በሽታ ቶሎ ቶሎ ሽንት የመምጣት፣ የረሃብ ስሜት፣ ቶሎ ቶሎ ውሃ የመጠማትና የመሳሰሉት ህመም ነክ ምልክቶችን ያሳያል፡፡ እርግዝናን ተከትሎ የሚመጣው የስኳር በሽታ ግን ይሄ ነው ተብሎ የሚገለፅ ምልክት አያሳይም፡፡

ጥያቄ፡- በእርግዝና ወቅት የሚከሰት የስኳር በሽታ ከወሊድ በኋላ የመቀጠል ዕድል አለው?
ዶ/ር፡- በእርግዝና ወቅት የተከሰተ ስኳር በሽታ ከወሊድ በኋላ ባሉት 6 ሳምንታት ይጠፋል፡፡ ነገር ግን ከእርግዝና በፊት ሳይታወቅ የነበረ የስኳር በሽታ ከሆነ፣ ከወሊድ በኋላም የስኳር መጠንን በአግባቡ መቆጣጠር ካልተቻለ በሽታው ይቀጥላል፡፡ በሌላም በኩል ከእርግዝና ጋር ተያይዞ የመጣ ስኳር በሽታ የነበረባቸው ሴቶች፣ ምንም እንኳን ከወሊድ በኋላ ህመሙ ቢጠፋም የተጠኑ ጥናቶች እንደሚያሳዩት ከ10 ዓመት በኋላ ወደ መደበኛው የስኳር በሽታ የመሸጋገር ዕድላቸው ከፍ ያለ ነው፡፡

ጥያቄ፡- ወደ ፅንሱ የመተላለፍ እድልስ አለው?
ዶ/ር፡- በእርግዝና ወቅት የሚከሰት የስኳር በሽታ፣ ከፍተኛ የግሉኮስ መጠን በሰውነት ውስጥ እንዲከሰት ያደርጋል፡፡ በዚህ ምክንያት ፅንሱ ከሚጠበቀው በላይ ፋፍቶ የሚወለድበት ሁኔታ ሰፊ ነው፡፡ ይህ ውፍረት ደግሞ በልጅነት ብቻ ተወስኖ የሚቀር ሳይሆን፣ በዕድሜ ዘመኑ ለከፍተኛ የውፍረት ችግር ይጋለጣል፡፡
በዚህም ሳቢያ ከስኳር በሽታ በተጨማሪ ለደም ግፊት፣ ለልብ ህመም፣ ለስኳር እና ለደም ግፊት በሽታ የመጋለጥ ዕድል አለው፡፡ በሌላም በኩል በመጀመሪያው የእርግዝና ወቅት የተከሰተ የስኳር በሽታ ከሆነ ፅንሱ ለነርቭ ስርዓት፣ ለአዕምሮ፣ ለልብና ለህብለ ሰረሰር የአፈጣጠር ችግር ይከሰትበታል፡፡ ስለሆነም በእርግዝና ወቅት የሚከሰት ስኳር በሽታ፣ በፅንሱ ላይ የሚያስከትለው ችግር ከወሊድ በኋላ የሚቆም ሳይሆን እስከ ህይወት ዘመኑ የሚቀጥል እንደሆነ መገንዘብ ይገባል፡፡ በየጊዜው ተገቢው የህክምና ክትትል መደረግም ይኖርበታል፡፡

ጥያቄ፡- በእናትየዋ ላይ የሚከሰት ጤና ነክ ችግር ካለ ቢገልፁልኝ?
ዶ/ር፡- በወቅቱ ያልታከመና በቁጥጥር ስር ያልዋለ ስኳር በእናትየዋ ላይ የሚያስከትለው የጤና ችግር ሰፊ ነው፡፡ በተለይም የዓይን፣ የልብና የኩላሊት በሽታዎች እንዲሁም ከወሊድ ጋር የተያያዘ ከፍተኛ የደም መፍሰስና በቀዶ ህክምና ለመውለድ መገደድን ያመጣል፡፡

ጥያቄ፡- ህክምናውስ ምንድነው?
ዶ/ር፡- የስኳር በሽታ ህክምና ሶስት ነገሮችን የሚያካትት ነው፡፡ የመጀመሪያው አካላዊ እንቅስቃሴ ማድረግ ነው፡፡ አካላዊ እንቅስቃሴው በቀን ለ30 ደቂቃ እርምጃና መሰል ቀለል ያሉ አካላዊ እንቅስቃሴዎችን ማድረግ የስኳር መጠኑን ለማስተካከል ይረዳል፡፡ ሁለተኛው የህክምና አይነት የአመጋገብ ስርዓትን ማስተካከል ነው፡፡ ጣፋጭ ምግቦችን ከየዕለቱ የምግብ ገበታችን በማስወገድ የአሰር ምግብ ይዘት ያላቸውን ለምሳሌ የገብዝ ዳቦ፣ በቆሎ፣ እንጀራና አትክልት ምግቦችን ማዘውተር ጠቃሚ ይሆናል፡፡ የስኳር መጠኑ በዚህ ሂደት የማይተካከል ከሆነ የመድሃኒት ህክምና መጀመር ተገቢ ይሆናል፡፡ የመድሃኒት ህክምናው ኢንሱሊን መስጠት ነው፡፡ እናትየዋ ከምግብ በፊት፣ ከምግብ በኋላና ከሌሊቱ 6፡00 ሰዓት የስኳር መጠኗን በመለካት ተገቢው ክትትል ማድረግ ይኖርባታል፡፡ በአጠቃላይ ህክምናው ውጤታማ እንዲሆን እናትየዋ ከምንም በላይ ትኩረት ሰጥታ መስራት ይኖርባታል፡፡

ጥያቄ፡- በእርግዝና ወቅት ኢንሱሊን መስጠት ችግር የለውም እንዴ?
ዶ/ር፡- በመድሃኒት መልክ የሚሰጠው ኢንሱሊን፣ በሰውነት ውስጥ ያለውን አይነት አስተዋፅኦ ስለሚያደርግ የበለጠ ጠቃሚ ነው፡፡ መድሃኒቶችን የምንሰጠው ከጉዳታቸው ጥቅማቸው ሲያመዝን ነው፡፡ የኢንሱሊን መድሃኒት ክትትል ከወለደችም በኋላ የስኳር መጠኑ እስኪስተካከል ድረስ ተጠናክሮ መቀጠል ይኖርበታል፡፡

The post Health: እርግዝናና የስኳር በሽታ (ከህክምና ባለሙያ ጋር የተደረገ ቃለምልልስ) appeared first on Zehabesha Amharic.

በሌሉበት ሞት የተፈረደባቸው የደርግ አባል በሆላንድ ታሰሩ * በጎጃም በርካታ ሰዎች እንዲረሸኑና በጅምላ እንዲቀበሩ አድርገዋል ተብሏል

$
0
0

Zehabesha News
በደርግ የአገዛዝ ዘመን ዜጎችን በመግደል፣ በማሰርና በማሰቃየት ተከስሰው ሞት የተፈረደባቸው አንድ ስማቸው ያልተገለጸ የቀድሞ የደርግ ባለስልጣን፤ በሆላንዷ ከተማ አምስቴልቪን በፖሊስ ቁጥጥር ስር መዋላቸውን ኤንኤል ታይምስ የተባለው የአገሪቱ ድረገጽ ትናንት ዘገበ፡፡

በሆላንድ የሚገኘው የአለማቀፍ ወንጀሎች ምርመራ ቡድን አቃቤ ህግ፣ ግለሰቡ እ.ኤ.አ በ1978 ባስተላለፉት ትዕዛዝ፣ በጎጃም አካባቢ ታስረው የነበሩ በርካታ ሰዎች ተረሽነው አስከሬናቸው በጅምላ መቃብር እንዲቀበር ተደርጓል ማለታቸውን ዘገባው ገልጧል፡፡ተጠርጣሪው ከሁለት ሳምንታት በፊት በፖሊስ ቁጥጥር ስር እንደዋሉ የጠቆመው ዘገባው፣ አምስቴልቪን ከተማ ውስጥ በሚገኘው የግለሰቡ መኖሪያ ቤት ውስጥ በተደረገ ፍተሻ የተለያዩ ማስረጃዎች የተገኙ ሲሆን በሄግ የሚገኘው ፍርድ ቤትም ከትናንት በስቲያ በዋለው ችሎት፣ ግለሰቡ ለ90 ቀናት በእስር ላይ እንዲቆዩ ወስኖባቸዋል ብሏል፡፡የሆላንድ ፖሊስ ግለሰቡ የተጠረጠሩባቸውን የወንጀል ድርጊቶች ስለመፈጸማቸው ምርመራ ማድረግ መጀመሩን ዘገባው ገልጾ፣ ፖሊስም የምስክሮችን ቃል መቀበሉንና ተጠርጣሪው ድርጊቶቹን ስለመፈጸማቸው ምስክርነታቸውን ከሰጡ ግለሰቦች አብዛኞቹ በውጭ አገራት የሚኖሩ ኢትዮጵያውያንን እንደሆኑ አስታውቋል፡፡ምስክሮቹ በሰጡት ቃል ግለሰቡ በጎጃም አካባቢ የደርግ ባለስልጣን ሆነው ባገለገሉባቸው አመታት የተጠቀሱትን የወንጀል ድርጊቶች ስለመፈጸማቸው ተናግረዋል ያለው ዘገባው፣ የሆላንድ የወንጀል ምርመራ ባለስልጣናትም ግለሰቡን ለሞት ቅጣት ያበቃቸውን የወንጀል ክስ የተወሰነ መረጃ ከኢትዮጵያ መንግስት ባለስልጣናት መረከቡን ገልጧል፡፡የአለማቀፍ ወንጀሎች ምርመራ ቡድን፣ በደርግ የአገዛዝ ዘመን በደብረ ማርቆስና በመተከል እስር ቤቶች ውስጥ የግድያና የስቃይ ድርጊቶችን በፈጸሙ ግለሰቦች ላይ ትኩረት በማድረግ ምርመራ እያደረገ እንደሚገኝ ዘገባው አስታውቋል፡፡

61 አመታቸው እንደሆነ የተነገረላቸው እኒሁ ባለስልጣን፤ ከጥቂት አመታት ወዲህ ነዋሪነታቸውን በሆላንድ እንዳደረጉና የአገሪቱ ዜግነት እንደተሰጣቸው ያስታወሰው ዘገባው፣ ግለሰቡ በኢትዮጵያ ፍርድ ቤት በሌሉበት የእድሜ ልክ እስራትና የሞት ቅጣቶች እንደተጣሉባቸውም ገልጧል፡፡

Source: Addiss Admass Newspaper

The post በሌሉበት ሞት የተፈረደባቸው የደርግ አባል በሆላንድ ታሰሩ * በጎጃም በርካታ ሰዎች እንዲረሸኑና በጅምላ እንዲቀበሩ አድርገዋል ተብሏል appeared first on Zehabesha Amharic.

ሕጉ ለበፍቃዱ ነው –ውሳኔውስ?

$
0
0

ከዞን 9 ማስታወሻ የተገኘ

የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት፣ ልደታ ምድብ፤ 19ኛ ወንጀል ችሎት በስድስት ጦማርያን እና በሶስት ጋዜጠኞች ላይ በ08/11/2006ዓ.ም ከፍትህ ሚኒስትር የቀረበለትን ክስ በቀን 11/11/2006 በይፋ አንብቦ ክሱን ከከፈተ ወዲህ መሰረታዊ ውሳኔ ያሳለፈው ጥቅምት05/2008 ነው ማለት ይቻላል፡፡ ይሄውም ክሳቸው በሰኔ 30/2007 ተቋርጦ ከተፈቱት ሶስት ጋዜጠኞች እና ሁለት ጦማርያን ውጭ ክሳቸው ቀጥሎ ከነበሩት አምስት የዞን ዘጠኝ ጦማርያን መካከል አራቱ መከላከል ሳያስፈልጋቸው በነፃ እንዲሰናበቱና ከጦማርያኑ መካከል በፍቃዱ ሃይሉ ግን የፀረ-ሽብርተኝነት ሕጉ ተጠቅሶበት የተከሰሰው ክስ ተሰርዞ በመደበኛው ወንጀል ሕግ አንቀፅ 257/ሀ መሰረት‹‹[ሕገ መንግስቱንና ሕገ መንግስታዊ ስርዓቱን በሃይል የመናድ ወንጀል] … እንዲፈፀም ለማድረግ … በንግግር፣ በሥዕል ወይም በፅሁፍ አማካይነት በግልፅ የመቀስቀስ ወንጀል ክስ›› በሚል ተሻሽሎ ክሱን እንዲከላከል ብይን መስጠቱ ነው፡፡

(ጋዜጠኛ በፈቃዱ ኃይሉ)

(ጋዜጠኛ በፈቃዱ ኃይሉ)

ነፃ የተባሉትና በአሁኑ ወቅት በእስር ላይ የሚገኙት አቤል ዋበላ፣ አጥናፉ ብርሃኔና ናትናኤል ፈለቀ ምንም እንኳን ፍርድቤቱ ከእስር እንዲፈቱ ትዕዛዝ ቢያስተላልፍም ይህ ፅሁፍ እስከወጣበት ጊዜ ድረስ አልተፈቱም፡፡ አቃቤ ሕግ እግድ አስወጥቶ ይግባኝሊጠይቅባቸው ይችላል የሚል ከፍተኛ ግምትም በብዙዎች ዘንድ አድሯል፡፡ ይሄም በትናንትናው እለት በፍርድ ቤቱ የተሰጠውን ‹የነፃናቸው› ውሳኔ ትርጉም አልባ የሚያደርግና የጦማርያኑንም ሕገ መንግስታዊ መብት የሚጥስ ተግባር ከመሆን አይዘልም፡፡ (ይሄን ጉዳይበሚመለከት ሌላ ፅሁፍ ይዘን እንወጣለን)፡፡
በዚህ ፅሁፍ ለማየት የተሞከረው ግን ጦማሪ በፍቃዱ ሃይሉ ‹ተከላከል› ስለተባለበት ጉዳይ እና ለረቡዕ ጥቅምት10/2008 ለዋስትና ጉዳይ ስለተቀጠረው ጉዳይ ነው፡፡ በፍቃዱ የሚከላከለው ምኑን ነው የሚለውን የፍሬ ነገር (substantive)ጉዳይ በዚህ ፅሁፍ ለማየት አልተሞከረም፡፡ ይልቁንም የበፍቃዱ የዋስትና ጥያቄ ምላሽ ምን መሆን አለበት? እና በፍቃዱ የተከሰሰበት የሕግ አንቀፅ ምን ይነግረናል? ለሚለው ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት የተዘጋጀ ፅሁፍ ነው፡፡

ዋስትና ሕገ መንግስታዊ መብት ነው?

አዎ! የኢፌዴሪ ሕገ መንግስት በአንቀፅ 19 ላይ የተያዙ ሰዎች መብት ሲደነግግ፤ ንዑስ አንቀፅ 6 ላይ እንዲህ ይላል፡
የተያዙ ሰዎች በዋስ የመፈታት መብት አላቸው፡፡ ሆኖም በሕግ በተደነገጉ ልዩ ሁኔታዎች ፍርድ ቤት ዋስትና ላለመቀበል ወይም በገደብ መፍታትን ጨምሮ በቂ የሆነ የዋስትና ማረጋገጫ እንዲቀርብ ለማዘዝ ይችላል፡፡
ለመሆኑ በአንቀፁ እንደ ልዩ ሁኔታ (exception) ፍርድቤቱ ዋስትና ላለመቀበል የሚችልባቸውን ሁኔታዎች ምንድን ናቸው?

ዋስትና በኢትዮጵያ ሕግ በምን አግባብ ነው የሚፈቀደው? የሚከለከለውስ?

አንድ ሰው የተከሰሰበትን የወንጀል ክስ ከእስር ቤት ውጭ ሆኖ መከታተል ይችል ዘንድ እና ጥፋተኛ ላልተባለበት የወንጀል ድርጊት ታስሮ መቆየት ስለሌለበት ዋስትና ከታሰሩ ሰዎች መብቶች አንዱና ዋነኛው በመሆን ተደንግጓል፡፡ ነገር ግን ይህ ህገ መንግስታዊ መብት ለሁሉም ተከሳሾች እንዲሁ (for granted) የሚሰጥ አይደለም፡፡ ይልቁንም በኢትዮጵያ ሕግ ዋስትና የሚያስፈቅዱ (bailable)እና ዋስትና የሚያስከለክሉ (non-bailable) ወንጀሎች በተለያ ቦታዎች በግልፅ ተደንግገዋል፡፡ ዋስትና በመርህ ደረጃ የሚያስከለክሉወንጀሎች ምን አይነት ናቸው? የሚለውን ስንመለከት፤ በመጀመሪያ የምናገኝው የኢትዮጵያ የወንጀለኛ መቅጫ ሥነ ሥርዓት ሕግ ቁጥር63ን ሲሆን፣ በዚህ አንቀፅ ንዑስ ቁጥር 1 መሰረትም፡
befekadu
ማንኛውም የተያዘ ሰው የተከሰሰበት ወንጀል የሞት ቅጣትን ወይም አስራ አምስት ዓመት ወይም ከዚያ በላይ የሆነ ፅኑ እስራት የማያስቀጣው ከሆነና ወንጀል የተፈጸመበት ሰው በደረሰበት ጉዳት የማይሞት የሆነ እንደሆነ ፍርድ ቤቱ የዋስትና ወረቀት አስፈርሞ ለመልቀቅ ይችላል፡፡
ይህ ለሁሉም የወንጀል አይነቶች የሚሰራ መርህ ሲሆን አንድ ሰው የተከሰሰበት የወንጀል ድርጊት ከአስራ አምስት ዓመት ፅኑ እስራት በላይ የሚያስቀጣው በሆነ ጊዜ እና ወንጀል የፈፀመበት ሰው የሞተ እንደሆነ የዋስትና መብቱን ይነፈጋል ማለት ነው፡፡ከዚህ አጠቃላይ መርህ ባለፈ በተለያዩ ህጎች ላይ ዋስትና በመርህ ደረጃ ተከልክሎ እናገኘዋለን፡፡ በዚህም መሰረት በተሻሻለው የጸረሙስና ልዩ ስነ ስርአትና የማስረጃ ሕግ አዋጅ ቁጥር 434/1997 አንቀፅ 4 መሰረት የሙስና ወንጀል አስር ዓመትና ከዛ በላይየሚያስቀጣ ከሆነ ዋስትና ያስከለክላል ፡፡ እንዲሁም የሽብርተኝነት ወንጀልም በፀረ-ሽብርተኝነት አዋጅ ቁጥር 652/2001 አንቀፅ20 መሰረት ዋስትና የማያሰጥ እንደሆነ ተደንግጓል፡፡ እንግዲህ አሁን ባለው የኢትዮጵያ የሕግ ስርዓት የዋስና መብት በመርህ ደረጃ የሚከለከለው በነዚህ ሶስት ሁኔታዎች ብቻ ነው ማለት ነው፡፡

ይህ ማለትም በመርህ ደረጃ ዋስትናን ከሚከለክሉት የሕግ ድንጋጌዎች ውጭ ያሉ ሌሎች የወንጀል ክሶች ዋስትና የሚያስፈቅዱ(bailable) ናቸው ማለት ነው፡፡ እዚህም ላይ ግን ሌላ እቀባ አለ – የኢትዮጵያ የወንጀለኛ መቅጫ ሥነ ሥርዓት ሕግ አንቀፅ67፡፡ በዚህ የስነ ስርዓት ሕጉ አንቀፅ መሰረት አንድ ሰው የተከሰሰበት ወንጀል በመርህ ደረጃ ዋስትና የማያስከለክል ቢሆንም (ማለትም ከአስራ አምስት ዓመት ፅኑ እስራት በታች የሚያስቀጣ ቢሆንም፣ ከአስር ዓመት በታች የሚያስቀጣ የሙስና ወንጀል ቢሆንም፣ከሽብርተኝነት ወንጀል ውጭ ቢሆንም) ፍርድ ቤቱ በሶስት የተለያዩ ምክንያቶች ተከሳሹን ዋስትና ሊከለክለው ይችላል፡፡ ይሄውም፡
መጥፋት (Disappearance)፡ተከሳሹ በዋስትና ቢወጣ ይጠፋል ተብሎ ሲገመት፣
ማጥፋት (Commits another offense)፡ ተከሳሹ በዋስና ቢወጣ ሌላ ወንጀል ይፈፅማል ተብሎ ሲገመትና፣
አሁንም ማጥፋት (Witness Interference)፡ ተከሳሹ በዋስትና ቢወጣ ምስክሮች ላይ ጫና ይፈጥራል፣ ሌሎች ማስረጃዎችንም ያጠፋል ተብሎ ሲገመት ነው፡፡

ፍርድ ቤቱ ምንም እንኳን ተከሳሹ የተከሰሰበት የወንጀል ድርጊት በመርህ ደረጃ ዋስትና የማያስከለክል (bailable) ቢሆንም ከነዚህ ሶስት ምክንያቶች አንዱ አለ ብሎ ካመነ ተከሳሹን ፍርድ ቤቱ ዋስትና ሊከለክለው ይችላል፡፡

የበፍቃዱ የዋስትና ጉዳይ

እንግዲህ በመግቢያችን እንዳነሳነው ጦማሪ በፍቃዱ ሃይሉ ተከሶበት የነበረው የሽብርተኝት ወንጀልን ለመፈፀም ማቀድ፣ ማነሳሳት፣ መሞከር፣ መዘጋጀትና ማሴር ክስ ውድቅ ተደርጎ በፃፋቸው ፅሁፎች ‹‹[ሕገመንግስቱንና ሕገ መንግስታዊ ስርዓቱን በሃይል የመናድ ወንጀል]… እንዲፈፀም ለማድረግ … በንግግር፣ በሥዕል ወይም በፅሁፍ አማካይነትበግልፅ የመቀስቀስ ወንጀል›› ፈፅመሃል፣ ክሱንም ተከላከል መባሉን አይተናል፡፡ ታዲያ በፍቃዱ አሁን ተከላከል የተባለበትየወንጀል ክስ በፍቃዱን የዋስትና መብት ያስከለክለዋልን? ከላይ ካነሳናቸው አጠቃላይ የኢትዮጵያ የዋስትና ሕግ መርሆዎች አንፃር እንመልከት፡፡

የቀረበበት ክስ Bailable ነው ወይስ Non-bailable?
Bailable ነው፡፡ ምክንያቱም፡

አሁን በፍቃዱ ተከላከል የተባለበት የኢፌዴሪ የወንጀል ሕግአንቀፅ 257 በአጠቃላይ የሚያስቀጣው ከአንድ ቀን እስከ አስር ዓመት ፅኑ እስራት ሲሆን፤ የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ‹‹…ግልፅነትና ተጠያቂነትን ባረጋገጠ መልኩ ውጤታማና ተገማችነት ያለው ቅጣት የሚሰጥበትን ስርዓት…›› ለመመስረት በማሰብ በጥቅምት 2006 ዓ.ም ያወጣው የተሻሻለው የወንጀል ቅጣት አወሳሰን መመሪያ ቁጥር 02/2006 አንቀፅ 9 ላይ በማያሻማ ሁኔታ እንደደነገገው ደግሞ በፍቃዱ ሃይሉ የተከሰሰበት የኢፌዴሪ የወንጀል ሕግ አንቀፅ 257/ሀ ማለትም አጥፊው ድርጊቱን በንግግር፣ በስዕል፣ ወይም በፅሁፍ አማካኝነት በግልፅ የቀሰቀሰ እንደሆን የእስራት ቅጣቱ ሁለት እርከን ነው ይላል፡፡ ይሄም ማለት በመመሪያውአባሪ አንድ ላይ አንደተገለፀው እርከን ሁለት የሚያስቀጣው ከአስርቀን እስከ ስድስት ወር እስራት ብቻ ነው፡፡ በመሆኑም በፍቃዱ ጥፋተኛ እንኳን ቢባል ሊቀጣ የሚችለው ከፍተኛ ቅጣት የስድስትወራት እስራት ብቻ ነው፡፡ በአጠቃላይ በፍቃዱ የተከሰሰበት ወንጀል ከ15 ዓመት ፅኑ እስራት በላይ የሚለውን የመከልከያ መርህ አያሟላም፡፡
በበፍቃዱ ላይ ተመስርቶ የነበረው ‹የሽብርተኛ ድርጅት በማቋቋም የሽብርተኝነት ወንጀልን ለመፈፀም ማቀድ፣ ማነሳሳት፣ መሞከር፣ መዘጋጀትና ማሴር› ክስን ፍርድ ቤቱ ‹ዞን ዘጠኝ የሽብርተኛ ድርጅት አይደለም የጦማርያን እና የአራማጆች ቡድንእንጂ› በማለት በብይኑ በግልፅ ውድቅ ስላደረገው፤ የፀረ-ሽብርተኝነት ህጉ ከዚህ በኋላ በበፍቃዱ ላይ ተፈፃሚነት የለውም፡፡
ሶስተኛውና በኢትዮጵያ በመርህ ደረጃ ዋስትና የሚያስከለክለውየወንጀል አይነት ከአስር ዓመት ፅኑ እስራት በላይ የሚያስቀጣ የሙስና ወንጀል (grand corruption) ሲሆን፤ የበፍቃዱ ክስደግሞ ከሙስና ወንጀል ጋር ፈፅሞ ግንኙነት የሌለው ነው፡፤
በአጠቃላይ በመርህ ደረጃ በፍቃዱን ዋስትና ሊያስከለክል የሚችል ምንም አይነት የህግ አግባብ የለም፡፡

መርሁ ሲፈቅድ፤ ዳኝነቱ ይከለክለዋልን?
በፍፁም ሊከለክለው አይችልም፡፡ ምክንያቱንም እንመልከት፡፡
በኢትዮጵያ ሕግ ዋስትና በመርህ ደረጃ ተፈቅዶ በዳኞች ስልጣን (discretionary power) ሊከለከል የሚችልባቸውሶስት ምክንያቶች የኢትዮጵያ የወንጀለኛ መቅጫ ሥነ ሥርዓት ሕግ አንቀፅ 67 መደንገጉን ከላይ ተመልክተናል፡፡ የበፍቃዱን ጉዳይምከዚህ አንፃር ስንመለከት፡

‹ይጠፋል› ፡ ተከሳሾች ይጠፋሉ ተብለው የሚገመቱት በተከሰሱበት ድርጊት ጥፋተኛ ከተባሉውሳኔው የሚያስከትልባቸውን እስር ለማምለጥ እንደሆነ ይታወቃል፡፡ በፍቃዱ የተከሰሰበት የሕግ አንቀፅ (የወንጀል ሕጉ አንቀፅ257/ሀ) ሊያስቀጣ የሚችለው ከአስር ቀናት እስከ ስድስት ወራት እስራት ብቻ ሆኖ እያለ በፍቃዱ ደግሞ ከአንድ ዓመት ከስድስት ወራት በላይ በእስር ላይ ያለ ነው፡፡ ይሄም መታሰር ከሚገባው ከእጥፍ በላይ ታስሯል ማለት ነው፡፡ ታዲያ ለምን ይጠፋል?
ያጠፋል ፡ ተከሳሹ ቢፈታ ሌላ ጥፋት ያጠፋል ተብሎ ሲገመት ፍርድ ቤቱ ተከሳሹን ዋስትና ሊከለክለው ይችላል፡፡ ይህ ክልከላ በዋናነት ለደጋጋሚ ወንጀለኞች (recidivists) የተደነገገ ነው፡፡ በፍቃዱ እንኳን ደጋጋሚ ወንጀለኛ ሊሆን በሕይወት ዘመኑ አንድም ክስ ተመስርቶበት የማያውቅ መልካም ጠባይ ያለው ሰው ነው፡፡ በመሆኑም ቢፈታ ሌላ ወንጀል ሊፈፅም ይችላል የሚለው መከልከያ በፍፁም እሱ ላይ አይሰራም፡፡
አሁንም ያጠፋል ፡ ሌላው ዋስትና ሊያስከለክል የሚችለው ምክንያት ተከሳሽ ከእስር ቢፈታ እሱ ላይ ሊቀርቡ የሚችሉ ምስክሮችን እና ሌሎች ማስረጃዎችን ያጠፋል ተብሎ ሲገመት ነው፡፡ በፍቃዱ ላይ ደግሞ ዓቃቤ ህግ አለኝ ያለውን ሁሉ ማስረጃ አሰምቷል/አቅርቧል፡፡ ሊጠፋ የሚችል ምንም ነገር የለምና እሱ ላይ ይሄ ምክንያት እይሰራም፡፡

በአጠቃላይ በፍቃዱ ሃይሉ የተከሰሰበት ወንጀል በመርህም ሆነ በዳኝነት ደረጃ ዋስትና ሊያስከለክል የሚችል አንዳችም ሕጋዊምክንያት የለውም፡፡ እንዲያውም የዋስትና መብቱን የሚከለክል አንዳችም ሕጋዊ ምክንያት ካለመኖሩም ሌላ የበለጠ የዋስትና መብቱንመከበር የሚገፋ ምክንያት አለ፤ ይሄውም በኢትዮጵያ ህግ አንድ ሰው ያላግባብ ለታሰረበት የእስር ጊዜ ካሳ የሚያስከፍል ስርዓት በሌለበት እና በፍቃዱ ደግሞ ጥፋተኛ እንኳን ቢባል ሊታሰር ከሚችለው ከአስር ቀናት እስከ ስድስት ወራት እስራት ከእጥፍ በላይ ታስሮ እያለአሁንም ዋስትና በመከልከል ሌላ ተጨማሪ እስር እንዲታሰር ማድረግ እጅጉን ኢፍትሃዊነት ከመሆኑም በላይ የወንጀል ህግ መርሆዎችን በሙሉ የሚገረስስ በመሆኑ ነው፡፡

257 – ያልተዘመረለት ሃሳብን የመግለፅ ነፃነት ጠላት

በፍቃዱ ሃይሉን ዋስትና ሊያስከለክል የሚችል አንዳችም ህጋዊ ምክንያት አለመኖሩን ከላይ ተመልክተናል፡፡ በዚህም መሰረት በፍቃዱ መብቱ ተከብሮለት በቀላል ዋስትና እንደሚወጣ ተስፋ እናደርጋለን፡፡ ነገር ግን ይሄን ፅሁፍ ከመቋጨታችን በፊት አሁን በፍቃዱ ተከላከል ስለተባለበት የኢፌዴሪ የወንጀል ሕግ አንቀፅ 257 ትንሽ ነገር ብለን እንጨርስ፡፡

የኢትዮጵያ መንግስት ላለፉት ስድስት ዓመታት የፀረ-ሽብርተኝነት ሕጉን አዋጅ ቁጥር 652/2001 ሃሳብን በነፃነት የመግለፅ መብትን ለመደፍጠጥ እየተጠቀመበት እንደሆነ ከተለያዩ አካላት ትችት እየተሰነዘረበት ይገኛል፡፡ የተለያዩ ጋዜጠኞች እና ፀሃፊዎችም የዚህ አዋጅ ሰለባ መሆናቸው በየቀኑ የምናየው እውነታ ነው፡፡ ነገር ግን ከዚህ አዋጅ ባለፈ በተለይ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ መደበኛውን የወንጀል ሕግ እንደገና ወደመጠቀሙ ያዘነበለ ይመስላል፡፡ ዋነኛው የህግ አንቀፅ ደግሞ የኢፌዴሪ የወንጀል ሕግ አንቀፅ 257 ነው፡፡

ይህ የሕግ አንቀፅ ተጠቅሶ ነው ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ላይ የሶስት አመት እስራት የተፈረደበት (ጥቅምት 2007)፣ይህ የሕግ አንቀፅ ተጠቅሶ ነው ማስተዋል አሳታሚ ድርጅት የአስር ሺህ ብር የገንዘብ ቅጣት ተቀጥቶ የተዘጋው ፣ ይህ የሕግ አንቀፅ ተጠቅሶ ነው የአዲስ ጉዳይ መፅሄት ስራ አስኪያጅ እና ጋዜጠኛ እንዳልካቸው ተስፋዬ ላይ የሶስት ዓመት ከሶስት ወራት እስራት የተፈረደበት (መስከረም 2007)፣ ይህ የሕግ አንቀፅ ተጠቅሶ ነው የሎሚ መፅሄት ዋና ስራ አስኪያጅና ጋዜጠኛ ግዛው ታየ ላይ የሶስት ዓመት ከሶስት ወራትእስራት የተፈረደበት (መስከረም 2007)፣ ይህ የሕግ አንቀፅ ተጠቅሶ ነው የፋክት መፅሄት ስራ አስኪያጅ ፋጡማ ኑሪያ ላይ የሶስትዓመት ከአስራ አንድ ወራት እስራት የተፈረደባት (መስከረም 2007)፣ ይህ የሕግ አንቀፅ ተጠቅሶ ነው የቀድሞው የዕንቁ መፅሄትዋና አዘጋጅና ጋዜጠኛ ኤልያስ ገብሩ ላይ ክስ ተመስርቶበት በአሁኑ ወቅት ክሱን እየተከታተል የሚገኘው … አሁን ደግሞ በፍቃዱ ሃይሉ በፃፋቸው ፅሁፎች ምክንያት ይህ የኢፌዴሪ የወንጀል ሕግ አንቀፅ 257 ተጠቅሶበት ተከላከል ተብሏል፡፡ የበፍቃዱን ከሌሎች ለየትየሚያደርገው በአንቀፁ ቀላል ቅጣት (ከአስር ቀናት እስከ ስድስት ወራት ብቻ) የሚያስከትለው አንቀፅ 257 ንዑስ አንቀፅ ‹ሀ› የተጠቀሰበት መሆኑ ነው፡፡

እንግዲህ ይህ የሕግ አንቀፅ ነው የቅርብ ጊዜ ሃሳብን ከመግለፅ ነፃነት ጋር በተያያዘ እየቀረቡ ላሉ ክሶች ዋነኛ መሰረትእየሆነ ያለው፡፡ በፍቃዱ ሃይሉም የቅርቡ አንቀጽ ሰለባ ነው፡፡

The post ሕጉ ለበፍቃዱ ነው – ውሳኔውስ? appeared first on Zehabesha Amharic.

በሚኒሶታ ለአርበኞች ግንቦት 7 ከ75 ሺህ ዶላር በላይ ተሰበሰበ

$
0
0

AG7

AG7 Minnesota
(ዘ-ሐበሻ) በሚኒሶታ ለአርበኞች ግንቦት 7 የገቢ ማሰባሰቢያ በተዘጋጀው ዝግጅት ላይ ከ7 ሺህ ዶላር በላይ መሰብሰቡን በስፍራው የነበሩት የዘ-ሐበሻ ዘጋቢዎች አስታወቁ::

እንደዘጋቢዎቻችን ከሆነ በክብር እንግድነት የአርበኞች ግንቦት 7 ንቅናቄ የውጭ ጉዳይ አመራር የሆኑት አቶ ነአምን ዘለቀ የተገኙ ሲሆን በትኬት ሽያጭ; በስጦታና በጨረታ ከ75 ሺህ ዶላር በላይ መሰብሰቡን አስተባባሪዎቹ ገልጸዋል::

የሚኒሶታው የአርበኞች ግንቦት 7 ስብሰባ በጋዜጠኞች ቭዲዮ እንዳይቀረጽ የተከለከለ በመሆኑ ዘ-ሐበሻ በቭዲዮ ንግግሮችን ለማቅረብ ባትችልም የስብሰባውን ዝርዝር ሁኔታ በስፋት ከሰዓታት በኋላ ታቀርባለች::

The post በሚኒሶታ ለአርበኞች ግንቦት 7 ከ75 ሺህ ዶላር በላይ ተሰበሰበ appeared first on Zehabesha Amharic.

ኢሕአዴግ ከዘር ፖለቲካ መዉጣት እንዳለበት ነበር የመከሩት ፖል ሄንዚ –ግርማ ካሳ

$
0
0

የአቶ መለስ ወዳጅ እና ልዩ አማካሪ የነበሩ፣ በአለም አቀፉ ማህበረሰብ ዘንድ ለኢሕአዴግ ተሟጋችና «ጠበቃ» ተብለው ይቆጠሩ ከነበሩ ጥቂት ግለሰቦች መካከል በቀዳሚነትና በዋናነት የሚጠቀሱ አሜሪካዊዉ ፖል ሄንዚ ነበሩ። እኝህ ሰው በምርጫ ዘጠና ሰባት ወቅት በኢትዮጵያ የተፈጠረዉን ሁኔታ ከግምት ዉስጥ በማስገባት፣ አቶ መለስ በሕይወት የነበሩ ጊዜ ኢሕአዴግን የመከሩት አንዳንድ ምክሮች ነበሩ።
Girma kassa
«ከ1991 በሁዋላ የተፈጠረዉ የፖለቲካ ስርዓት ብዙ ያልተጠና (Ad Hoc) እና ደርግ ሲወድቅ የነበረዉን ሁኔታ ያንጸባረቀ ነበር። ነገር ግን የማይቀየርና የማይሻሻል ተደርጎ ሊወሰድ አይገባዉም። ለምን ብዙ ጠቃሚ ያልሆኑ ሁኔታዎች እንዲከሰቱ አድርጓል» በማለት ነበር ፓል ሄንዝ የጻፉት።

ጠቃሚና አላስፈላጊ ካሉዋቸው ነጥቦች መካከል፣ በኢሕአዴግ ስርአት ከመጠን ያለፈ ጊዜና ጉልበት ለብሄር ብሄረሰቦች በደልና ብሶት መሰጠቱ እንዲሁም የትኩረት አቅጣጫዉ ከልክ ባለፈ መልኩ በብሄር ብሄረሰብ ወይንም በዘር ላይ መሆኑ ይገኙበታል።

በዚህም ምክንያት ፖል ሄንዝ ፣ ኢሕአዴግ በዘር ላይ ከማተኮር በአንድነት ላይ ማተኮር እንዳለበት፣ በዘር ላይ የተመሰረቱ ድርጅቶች ግንባር መሆኑ ቀርቶ፣ የኢትዮጵያዉያንን በሙሉ ጥቅም ለማስጠበቅ የቆመ አንድ ሕብረ ሄራዊ ፓርቲ ቢሆን መልካም ሊሆን እንደሚችል ነበር የገለጹት።

“If a majority of EPRDF leadership agrees that the entire party structure of Ethiopia should be changed, they would be well advised to pre-empt Kinijit by announcing the transformation of EPRDF into a party with a new name and new character. Among names that could be considered most appropriate might simply be “Ethiopian Democratic Party (EDP)” which would declare adherence to a platform for protecting the unity and integrity of the country, furthering its development and modernization in all respects with a firm commitment to democracy. ” ነበር ያሉት እኝህ ምሁር።

በፕል ሄንዝ አስተያየት ላይ የራሳቸዉን ተጨማሪ አስተያየት የሰጡት በዉጭ አገር የሚኖሩ ፣ አፍቃሪ ኢሕአዴግ የሆኑት አቶ ሳሙዔል ገብሩ ሲጽፉ «The notion of placing one’s ethnic affiliation above one’s status as being an Ethiopian has plagued the country’s political development. Ethiopians tend to declare each other as either “the oppressed” or “the oppressor” without recognizing that at one point in our history we were all oppressed and oppressors » በማለት የአቶ ፖል ሄንዚ አስተያየቶች ይጋራሉ።

ኢሕአዴግ፣ ከአራት በዘር ላይ የተደራጁ ድርጅቶች ስብሰብ መሆኑ ከበፊትም እንደማይዋጥላቸው የገለጹት አቶ ሳሙኤል «I would rather have the EPRDF as a political party and that be it. Too much concentration on one’s ethnicity further divides Ethiopia’s unity» ሲሉ ኢሕአዴግ ማሻሻያዎች እንዲያደርግ ጥሪ አቅርበዉም ነበር::

እንግዲህ ኢሕአዴግ በምርጫ ዘጠና ሰባት የተመለከተዉን የሕዝቡን ስሜት አስተዉሎ፣ ኢትዮጵያዉያን የተዋለዱ፣ የተደባለቁ፣ ለመቶ አመታት ተከባብረዉ ተዋደዉ የኖሩ መሆናቸዉን ተረድቶ፣ እንዲሁም እንደ ፖል ሄንዝና እና አቶ ሳሙኤል ገብሩ ያሉ ያቀረቡትን አስተያየቶች ከግምት በማስገባት፣ ደረጃ በጠበቀ መልኩ ኢትዮጵያዉያንን በሚያስተሳሰርና በሚያቀራረብ አጀንዳዎች ዙርያ መስራት ብዙ ይጠበቅበታል።

አቶ መለስ በሕይወት እያሉ ሕወሃት፣ ኦህዴድ፣ የአማራዉና የደቡብ ድርጅቶች በመዋሃድ አንድ አህዳዊ ፓርቲ ሊሆኑ እንደሚችሉ አንዳንድ መረጃዎች ደርሰዉኝ ነበር። ይሄ ሂደት ከአቶ መለስ ዜናዊ ጋር አብሮ የሞተ እስኪመስል ድረስ ዘረኝነቱ ተባብሷል። እንኳን እነዚህ ደርጅቶች አንድ ፓርቲ ሊሆኑ ቀርቶ ጭራሹኑ በመካከላቸውም የዘር ግጭቶች እየተፈጠሩ እንደሆነ ነው የምንሰማው።፡ የአኖሌና የጨለንቆ የጥላቻ ሃዉልቶች እየተናናሰ ለመጣው ዘረኝነትና የጥላቻ ፖለቲካ ሌላው ማሳያ ናቸው።

አሁን ኢሕአዴግ በዘር ፖለቲካው ረገድ መፍትሄ ማምጣት ይቻል ዘንድ ከግንባርነት ወደ ዉህደት ቢሸጋገር ደርጅቱን የበለጠ ሊጠቅመው ይችላል ባይ ነኝ። ሆኖም ከአራት ድርጅቶች ግንባርነት ወደ አንድ ፓርቲ መዞር በራሱ መሰረታዊ ለውጥ ሊሆን አይችልም።

መሰረታዊ ለዉጥ ማለት እነ ፓል ሄንዚ እንደመከሩት ኢሕአዴግ የአገሪቷን በዘር ላይ ያተኮረ ሕገ መንግስት እንዲሻሻል በማድረግ ዙሩያ ቀዳሚ በመሆን እንቅስቃሴዎች ሲጀምር ነዉ።

The post ኢሕአዴግ ከዘር ፖለቲካ መዉጣት እንዳለበት ነበር የመከሩት ፖል ሄንዚ – ግርማ ካሳ appeared first on Zehabesha Amharic.

የመቶ አመቱ የቤት ስራ –  ይገረም ዓለሙ 

$
0
0

በቅድሚያ ፤ ብዕር እንደ ጠብ -መንጃ ታይቶ፤ መጻፍ አሸባሪ አሰኝቶ ለእስር የበቁት የዞን 9 ጦማሪያን ነጻ የመባላቸው ዜና አስደሳች ነው፡ይሁን እንጂ የእስር ቤቱን ቅጥር አልፈው እስካልወጡ ድረስ እነርሱንም ሆነ ቤተሰብ ወዳጅ ዘመድን እንኳን ደስ አላችሁ ለማለት ተሞክሮአችን አያስችለንምና እስኪወጡ መጠበቅ ሊኖርብን ነው፡፡

ከመነሻው ነጻነታቸው የሚታወቀው ጸኃፍት ነጻነት ዛሬ ይበልጥ የተረጋገጠ በመሆኑ በዚህ ጉዳይ ከዚህ በኋላ ለመከራከር የሚደፍር የሚኖር አይመስለኝም፡፡ በቂ ማስረጃ አለን በማለት ሲፎክሩ የነበሩት አቶ ኃይለማሪያምን ጨምሮ፡፡

36884-zone9-bloggers4

አነጋጋሪ የሚሆነው ግን ይህ ፍርድ የተሰጠው በችሎቱ ነጻነትና በዳኞቹ ድፍረት፤ወያኔ የሚፈልገውን ስለፈጸመ፤ተቃውሞው ስለበረታ፤ አቅጣጫ ለማስቀየስና ወቅታዊውን ትኩሳት ለማብረድ፤ወይንስ ሌላ የሚለው ነው፡፡ በመሆኑም የችሎቱን ውሳኔ በጥለቀት ልናየውና ከምንደሰትበት በላይ ልንማርበት የሚገባ ይመስለኛል፡፡ ወደ ዛሬ ጉዳየ ልግባ፡፡

እንደ ዛሬው ሳይሆን ወያኔና ሻዕቢያን መለየት በማይቻልበትና ሁለቱም አስመራና አዲስ አበባ ቤተ መንግስት መግባታቸው የፈጠረባቸው የፖለቲካ ስካር ባልተነነበት ወቅት ኢትዮጵያውያንን ተውአቸው የመቶ አመት የቤት ስራ ሰጥተናቸዋል ማለታቸውን የምንረሳው አይመስለኝም፡፡ ያ ሰጥተናቸዋል ያሉት የቤት ስራ ብሄር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ብለው በፈጠሩልን  ልዩነት ተከፋፍለንና  በየመንደራችን ተቧድነን ልዩነት እንድናቀነቅን፣ ከትናንት የሀገራችን ታሪክ ለማለያያ ያስችላል ብለው እየመዘዙ የሚነግሩንን እየተቀበልን  እንድንነታረክ፣በትናንት ተሸብበን በርስ በርስ ጥላቻ ተጋርደን ለዛሬ ምንም እነዳንሰራና ስለ ነገ አሸጋግረን እንዳናይ የሚያደርገን ነው፡፡ እኛ በዚህ በተሰጠን የቤት ስራ ተጠምደን ሰንዳክር እነርሱ የጫካ ስምምነታቸውን ከቤተ መንግሥት ሆነው ተግባራዊ ሊያደርጉ፤ የደም ትስስራቸውን በፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ጥቅም ሊያጠብቁና ሊያስጠብቁ ያለሙትም ነበር፡፡ ነገር ግን ፈጣሪ ኢትዮጵያን የዘነጋት ቢመስልም ጨርሶ አይረሳትምና እኛን እያጋጩ ሊኖሩ ያሰቡ እነርሱው ተጋጩና  10 አመትም ሳይቆዩ አያሌ ህይወት ለቀጠፈ የከፋ ጦርነት ተዳርገው ፍቅራቸው ያልበጀን  በጠባቸው  ለእሊቂት ዳረጉን፡፡

ወያኔ ከዛ ተምሮ ከጫካ ቅዠቱ ይወጣል፣ ከዘር ልክፍቱ ይገላገላል፣ ተብሎ ሲጠበቅ  ከጦርነቱ እፎይታ ባገኘ ማግስት ይበሱን  ባሰበት፡፡ ጦርነቱ አስገድዶት የዘመረውን አንድነት ረስቶ በጎሰኝነቱ ገፋበት፤  ያመነውን የኢትዮጵያን የረዥም ዘመን የነጻነት ታሪክ መልሶ ካደ፣ የጦርነቱን ድል የኢትዮጵውያን ሳይሆን የራሱ አደረገ፡፡  ከሻዕቢያ ጋር በጋራ የሰጡንን የመቶ አመት የቤት ስራም ለብቻው  ቀጠለበት፡፡ ይሄው ተግባሩም በሥልጣን ለመቆየት አበቃው፡፡

ወያኔ ይህን ማድረጉ ከዚህ ውጪ በሥልጣን መቆየት እንደማይችል በማወቁ፣ ለሱ ሥልጣን በህዝብ ፈቃድ ከኮሮጆ ውጤት የሚገኝ ሳይሆን የሞት ሽረት ጉዳይ በመሆኑ፤ከልዩነት አንጂ ከአንድነት፤ ከጸብ እንጂ ከፍቅር የማያተርፍ በመሆኑ  ነውና ወያኔን በቅጡ እስካወቅነው ድረስ ትናንት የፈጸማቸውም ሆኑ ዛሬም ሆነ ነገ የሚፈጽማቸው ድርጊቶቹ ብዙም የሚያስገርሙን አይደሉም፡፡ ሊሆኑም አይገባምም፡፡

ከማስገረም አልፎ አነጋጋሪና ጥያቄ አጫሪው ጉዳይ በማወቅም ይሁን ባለማወቅ ይህን የወያኔን የመቶ አመት የቤት ስራ ተግባራዊ በማድረግ ለወያኔ እድሜ መርዘም አስተዋጽኦ የሚያደርጉ ያውም ወያኔን በመቃወም መስዋዕትነት የሚከፍሉ ወይንም ተቀዋሚ ነን የሚሉ ወገኖች ጉዳይ ነው፡፡

የወያኔን አገዛዝ እንቃወማለን ብለው ፓርቲ መስርተውም ሆነ በየግላቸው አየታገሉ እንደሚገኙ የሚናገሩ  ወገኖች ከትናንት ታሪካችን በጎውን አዳብረን በጎ ካልሆነው ተምረንና ተራርመን  የትናንቱ ጥፋትም ሆነ ስህተት ዛሬ እንዳይደገም በመንገዳችንም ላይ  አንቅፋት እየሆነ እንዳያስቸግር ወደ ትውልድም አንዳያሸጋገር ማድረግ የሚቻልበትን መላ ሊመቱ በተገባ ነበር፡፡ ነገር ግን ላል የማይባል ቁጥር ያላቸው ወገኖች በአያት ቅድመ አያቶቻችን ግዜ የተሰሩ ተብለው የተጻፉ ወይንም የተወሩ ነገሮችን እየመዘዙ መካሰስ መወቃቅስን ስራ ብለው ተያይዘውታል፡፡ ይህም የወያኔን የመቶ አመት የቤት ስራ መስራትና እንቃወመዋለን ለሚሉት ሀይል እድሜ መርዘም መጠቀም ነው ፡፡

ትኩረቱን ምርጫ 2007 ላይ አድርጎ ረገብ ያለ መስሎ የነበረው በዛሬ ላይ ሳይሆን በትናንት ትናንት በስቲያ ድርጊቶች ላይ መነታረክና ሲብስ መዘላለፍ ከምርጫው በኋላ ተባብሶ ቀጥሎአል፡፡ ከዛ በፊት ብዙም ጎልቶ አይሰማ የነበረ አማራነትም ተስፋፍቷል፡፡በማህበራዊ መገናኛዎች የሚጻፉትን ለተመለከተ አንዳንዶች ሌት ተቀን የሚያስቡት ስለ ልዩነት ይመስላል፡፡

ኢትዮጵያ ለሶስት ሺህ ዘመን የዘለቀው የነጻነት ታሪኳ ምንም እንከን ያልነበረበት ነው ብሎ የሚከራከር ያለ አይመስለኝም፡፡በታሪክ ውስጥ ለጥሩውም ሆነ ለመጥፎው ግንባር ቀደም ተጠቃሾች መኖራቸውም አሌ አይባልም፡፡እነዛ አባት እናቶቻችን ደግሞ አልፈዋል፡፡ እናም በጎ ተግባራቸውን እያወደስንና አጠንክረን እየቀጠልን ለትውልድ አንዲተላለፍ ማድረግ ፣ጥሩ ላልነበረው ታሪካችን  ደግሞ አሁን ተጠያቂም ተከሳሽም የሚሆን የለምና ሂሳብ ለማወራረድ ሳይሆን ለመተማመንና ለዛሬ መንገዳችን አንቅፋት እንዳይሆን፤ ለትውልድም እንዳይተላለፍ ለማድረግ አንድ ቦታ ለማቆም የሚያስችል መላ መምታት ነው የሚበጀው፡፡

ለችግሮች መፍትሄ መፈለግ ሲያቅት ወይንም የነበሩ ችግሮችን አግዝፎና አክፍቶ በማውራት ትርፍ የሚገኝ መስሎ ሲታሰብ ስራው ሁሉ የመፍትሄ ሀሳብ ሳያቀርቡ እነዛኑ ችግሮች መልሶ ቀልሶ ማውራት ይሆናል፡፡ ይህን በማድረግ የወያኔን እድሜ ከማራዘም ውጪ አንድ ስንዝር ውጤት ባለፉት ሀያ አራት ኣመታት አልታየም፡፡ነገር ግን ሂደቱ ቀጥሏል፡፡ እንደውም በአደገኛ ሁኔታ ወደ ወጣቱ ተሸጋግሯል፡፡

የትናንት ድርጊት ለአሁኑ ትውልድ መማሪያ እንጂ መነታረኪያ መሆን አልነበረበትም ፡፡ ትናንት ለዛሬ መጥፎውንም ሆነ ጥሩውን አውርሶ አልፏል፡፡ ሀገር የሚያድገው ከትናንት ጥሩውን አዳብሮ መጥፎውን አርሞ፤የጎደለውን አሟልቶ፤ ከዘመኑ ጋር እየተራመዱ በመስራት እንጂ የትናንቶቹ በዘመናቸው የሰሩትን እያነሱ በመውቀስና በመካሰስ አይደለም፡፡

መክሮ የሚመልስ ሽማግሌ ጠፍቶ፤አስተምሮም ሆነ ገዝቶ የጥፋትን መንገድ የሚያስቆም የሀይማኖት አባት ከእየእምነቱ ታጥቶ፤ በትናንት ታሪክ ተግባብቶ ለዛሬ ተግባር መተማመን ለመፍጠር የሚያስችል ተግባር የሚከውኑ ምሁራንና ፖለቲከኞች አልታይ ብለው ወዘተ  ስራችን በአብዛኛው ካለፈውና ካለው የበሳ ችግር ሊያመጣ የሚችል ሆኗል፡፡

ልዩነታችን ጌጣችን፣ አንድነታችን ኃይላችን መሆኑን አምነን በጋራ ሊያስኬደን የሚችል የመስማሚያ መንገድ ከመቀየስ ይልቅ ሆድና ጀርባ የሚያደርገንን ነገር መፈለጉ ለምን እንደሚቀለን ግራ ያጋባል፡፡ ከየትውልድ ድርሻን አንዱንም  ሳንከውን ሌላው ቢቀር ነጻነቷ የተከበረ ዳር ደንበሯ የታፈረ ሀገር ያቆዩንን አያት አባቶቻችንን ለማውገዝና በእነርሱ የተሰራውን ለመኮነን ልበ ሙሉ ደፋሮች መሆናችን ያስገርማል፡፡ ከአባቶቻችን የተረከብናትን ሀገር የህግ የበላይነት የተረጋገጠባትና ሰብአዊ መብት የተከበረባት ዴሞክራሲያዊት ሀገር ማድረግ ቀርቶ በተረከብናት ወርድና ስፋት ማቆየት ያልቻልን ትውልዶች የትናንቶቹን ለመውቀስ ለመክሰስ አንዴት እንደፍራለን፡፡ ዛሬ ሊኖረን የሚገባውን መልካም ግንኙነት ትናንትን እየጠቀስንና እያወሳን ማበላሸትና በጥርጣሬ እየተያየን ሆድና ጀርባ ሆነን እንድንቆም ስናደርግ ወያኔ የሰጠንን የመቶ አመት የቤት ስራ  እየሰራን መሆናችንን አስበነው እናውቅ ይሆን፡፡

ስነ ልቦናችንን ያጠናው ደካማ ጎናችንንም የተረዳው ወያኔ በየግዜው አዲስ የሚመስሉ ግን ያልሆኑ ነገሮችን እየሰጠን፤ እንዲሁም እኛኑ መስለው ቁስላችንን እያከኩ የሚያደሙ አርበኞችን በመካከላችን እያስገባ፤ ልዩነታችን አንዲሰፋ ቅራኔያችን አንዲባባስ በማድረግ እድሜውን አስረዝሟል፡፡

በምንም ሁኔታ ግን ለዚህ ተግባራችን ወያኔን ተጠያቂ ማድረግ የለብንም፡፡ ምክንያቱም የመቶ አመት የቤት ስራ ሰጥቻቸዋለሁ ሲል ምን እንደሆነና እንዴትና በምን ሁኔታ ተግባራዊ እንደሚያደርገው ተገንዝቦ ከወጥመዱ ማምለጥ የእኛ ድርሻ ነውና፡፡ ይም ቢቀር ሀያ አራት ዓመት ቀላል ግዜ አይደለምና በተግባር ከሚፈጽመው ተረድተን ከራሳችን አድራጎትም ተምረን የወያኔን የቤት ስራ በመስራት ለእሱ ዕድሜ አራዛሚ ካደረገን ተግባራችን መታቀብ መቻል የእኛ ስራ ነውና፡፡

ስለሆነም በትናንት እየተነታረክን የዛሬ መንገዳችንን ከማደነቃቀፍና የነገውንም ተስፋ ከማጨለም በትናንት ተነጋግሮ መተማመን የሚፈጠርበት ለወደፊቱም  በመተማመንና በመከበባር  በእኩልነት መኖር የሚስችል ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ለመመስረት  መትጋቱ ነው የሚበጅ፡፡ እንጅማ ወያኔ በሰጠን የመቶ አመት የቤት ስራ ባለፈ ነገር እየነታረኩ ከወያኔን አገዛዝ መላቀቅ የማይታሰብ ነው፡፡ ለመሆኑ የቱ ይቀድማል ያለፈው ሥርዓት  በአያት አባቶቻችን ላይ አደረሰ የሚባለው ወይንስ የዛሬው ገዢ በእኛ ላይ የሚያደርሰው ፡፡

የዘር ዝናር የታጠቀ ሳይሆን ኢትጵያዊ ግርማ ሞገስ የተላበሰ፣በጠብ-መንጃ ሳይሆን በምርጫ ኮሮጆ ውጤት ለሥልጣን የበቃ በሕዝብ የታመነና በህዝብ የሚተማመን ዴሞክራሲያዊ መንግሥት መመስረት ቢቻል ፤ ሀገራዊ መሰረቶችን ለማጽናት፤እኩልነትን ለማረጋገጥ፤አብሮነትን ለማጎልበት ወዘተ የሚነሱ ጥያቄዎች ሁሉ ይመከርባቸዋል መልስ ይፈለግላቸዋል፤ በዚህም የታሪካችን መጥፎ ገጽታ ወደ ትውልድ እየተሸጋገረ የልዩነት ምክንያት መሆኑ አንዲያበቃ በመተማመን  ቤተ መዘክር እንዲቀመጥ መልካሙም እንዲጎለብት ማድረግ ይቻላል፡፡ ስለሆነም ለዛ የሚያበቃንን ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ማግኘት  ቀዳሚው አጀንዳ ቢሆንስ?

The post የመቶ አመቱ የቤት ስራ –   ይገረም ዓለሙ  appeared first on Zehabesha Amharic.

“ቤተክርስቲያኒቱ አጠቃላይ ተቋማዊ ለውጥ ያስፈልጋታል” –ዲያቆን ዳንኤል ክብረት

$
0
0

ውድ የዘ-ሐበሻ አንባቢዎች ዛሬ እንደተለመደው የዲያቆን ዳንኤል ክብረት ዕይታ ሳይሆን የቃለምልልስ ዕይታውን ነው የምናስነብባችሁ:: ሃገር ቤት ከሚታተመው የቀለም ቀንድ ጋዜጣ ካደረገው ሰፋ ያለ ጉዳይ ለወቅታዊ ጉዳዮች ለአንባቢዎች ምላሽ ይሆናል ያልነውን አስተናግደናል::

daniel

እንደቤተ ክርስቲያን ተመራማሪና እንደ አገልጋይ ይመለከተወታል ብለን ስለምናስበው ርእሰ-ጉዳይ አንዳንድ ነጥቦችን እናንሳ፤ እንደሚያውቁት በቤተ ክርስቲያን አካባቢ ያለው ሙስና በብዙ መገናኛ ብዙኃን ሲዘገብ ቆይቷል። ጉዳዩ ካመት ዓመት ከመሻሻል ይልቅ ተባብሶ እንደቀጠለ ነው። ለመሆኑ ምዕመናንን ያስተምራሉ፣ ምሳሌ ይሆናሉ የሚባሉት አባቶች ራሳቸው በዚህ አሳፋሪ ተግባር ላይ መዘፈቃቸው እንዴት ይታያል? በዚህ ይዞታው የሚያስተምሩት ሕዝብስ እንዴት ሊሰማቸውና ሊቀበላቸው ይችላል? ለቤተ ክርስቲያኒቱስ አደጋ አይደለምን?

እንደኔ መረዳትና ጥናት ቤተ ክርስቲያን አሁን የተጋረጠባት አደጋ ከሁለት ነገሮች የመጣ ነው። አንደኛው ቤተ ክርስቲያኒቱ ዘመናዊውን ዓለም የተቀላቀለችበት መንገድ የፈጠረው ችግር ነው። የጥንቷ ቤተ ክህነት በተለይም ከ1950ዎቹ በፊት የነበረችው ቤተ ክህነት ከቤተ መንግሥቱ ጥግ ነበረች። አብዛኛው ሥራዋ መሬት ተኮር ነበር፤ ወደ ዘመናዊው የንግድ ዓለም አልገባችም ነበር። ለምታስተዳድረው መሬትም ከገበሬው የወጡት ቀሳውስት በቂ ነበሩ። እንዴት መሬት ማስተዳደር እንዳለባቸው በደንብ ያውቁ ነበር። በተጨማሪም በወቅቱ ለነበሩት ሥራዎች የሚበቃ የሰው ኃይልም ነበራት። ዘመናዊ ቤተ ክህነት ሲቋቋም ግን ለዘመናዊ ሥራ የሚሆን የሰው ኃይል አላደራጀችም። ለምሳሌ የቤተ ክርስቲያን ገንዘብ አያያዝ (Church Ac- counting) ትምህርት በየትኛው የቤተ ክርስቲያን ተቋም አይሰጥም። ዘመናዊ የቤተ ክርስቲያን አስተዳደር ትምህርት ቤተ ክርስቲያኒቱ አትሰጥም። የቀድሞው ፍትሐ ነገሥት ቢኖርም በቤተ ክርስቲያን ዘመናዊ ሕግን የሚመለከት ትምህርት አሁን አይሰጥም። የንግድ ተቋማቷን ያለምንም ሙያ ነው የምታስተዳድረው። ስለዚህ ‹‹ለምን ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ችግር ተፈጠረ?›› ብለን ስንነጋገር ችግሩ ያለው ከዚሁ ውስጥ ነው። ድጓው ውስጥ፣ ቅኔው ውስጥ፣ ቅዳሴው ውስጥ፣ ማህሌቱ ውስጥ፣ ሰዓታቱ ውስጥ ምንም ችግር የለም። ለዚህ የሚሆን በቂ የሰው ኃይልና በቂ ልምድ አላት። ዘመናዊ ተቋም የሚያስፈልጋት ዘመኑ ላመጣቸው አዳዲስ ዕውቀቶች ነው። ያልተማሩ ወይም ለነዚህ ዘመናዊ አሠራሮች ሙያ የሌላው ሰዎች ሲሰማሩ ክፍተት ተፈጠረ። በቢሊዮን የሚቆጠር የቤተ ክርስቲያኒቱን ሀብት የሚመሩ ሰዎችን ብትመለከት ለቦታው የሚመጥን ዕውቀት የላቸውም። ድጓ፣ ቅኔ፣ አቋቋም ወዘተ. ተምረህ ቢሊዮን ገንዘብ ልታንቀሳቅስ አትችልም። የሙያ ክፍተት ይፈጥራል።

ሁለተኛው ችግር ደግሞ የቤተ ክርስቲያኒቱ የፖሊሲ ችግር ነው። ቤተ ክርስቲያኒቱ ‹‹ምን ተግባር ላይ ነው የምሰማራው? ምን ላይ ነው የማልሰማራው? የትኛውን ነው የምሠራው? የትኛውን ነው የማልሠራው? የትኛው ይገባኛል? የትኛው አይገባኝም?›› የሚል ፖሊሲ ማውጣት አልቻለችም። ለምሳሌ ቤተ ክርስቲያን አካባቢ ከምናያቸው የንግድ ተቋማት ውስጥ አብዛኞቹ ሱቆች ናቸው። ቤተ ክርስቲያን ‹‹በእንዲህ ዓይነት ንግድ ውስጥ መግባት አለባት? የለባትም?›› ያከራክራል፤ ፖሊሲ የላትም። ብዙ ትምህርት ቤቶች ከፍታለች፤ የትምህርት ፖሊሲ ግን የላትም። የጤና ተቋማት ከፍታለች፤ የጤና ፖሊሲ ግን የላትም። ሌሎችንም ተቋማት ከፍታለች፤ ነገር ግን ምንም ፖሊሲ የላትም። የቀድሞ ትምህርት ቤቷችን የምታስተዳድርበት እኮ ያልተጻፈም ቢሆን የተለመደ አሠራር አላት። ስለዚህ ቤተ ክርስቲያኒቱ አሁን የምትወቀስበት እነዚህን ዘመኑ አምጥቶ የጨመረባትን ነገሮች በአግባቡ ማስተናገድ ባለመቻሏ ነው እንጅ ነባርና ልምድ ያካበተችባቸወን ዘርፎች በሚገባ ነው የምትከውናቸው። ይህ ምን አስከተለ? በቤተ ክርስቲያኒቱ ላይ የሚንጠላጠሉ ሰዎችን ፈጠረ።

አሁን ያለው ችግር ግን የዕውቀት ችግር ብቻ ነው ማለት ይቻላል?

የዕውቀት ችግር ብቻ አይደለም። ወደዚህ ቦታ የምታሰማራቸዉን ሰዎች መርጠህ አዘጋጅተህ የማሰማራት ችግር አለ። ይህ ተቋማዊ ችግር ነው፤ የቤተ ክህነት ተቋማዊ ኪሳራ ነው። ዛሬ አንድ መርጌታ ልቅጠር ብትል ችግር የለም። አንድ አገልጋይ ካህን ለመቅጠር ብትል በቂ የሰው ኃይል አለ። ነገር ግን በሥነ ምግባሩ የተመሰገነ፣ በቂ ዕውቀት ያለው እያልክ በመስፈርት የቤተ ክርስቲኒቱን ሀብት የሚያስተዳድር ሰው ለመቅጠር ችግር ነው። አይገኝም። አንድ ሰው ቅኔ ማህሌት ቁሞ ቢያበላሸዉ በሁሉም አቅጣጫ ‹‹እንደሱ አይደለም!›› የሚለው ሰውብዙነው።ነገርግንየቤተ ክርስቲያኒቱ ዘመናዊ አስተዳደር ሲበላሽ ‹‹እንደሱ አይደለም፤ አይሆንም!›› የሚል ሰው ጠፍቷል። ለዚህ የሚሆን በቂ ዕውቀትና በቂ ሥርዓት አልተዘረጋም። ያለ ፋይናንስ ፖሊሲ በቢሊዮን የሚቆጠር ገንዘብ የሚያስተዳድር ተቋም ከቤተ ክህነት ውጭ የለም። አሁንም እኮ እንደ ድሮው ሞዴል 16፣ ሞዴል 30 እየተባለ ነው የሚሠራው። በ21ኛው ክፍለ ዘመን በኮምፒዩተር ዘመን የዚህ ዓይነት አሠራር እንዴት ያስኬዳል? ሥርዓቱ በራሱ ለቁጥጥር ሳይሆን ለመብላት የተመቸ ነው። እንዲበላ ተብሎ የተዘጋጀ አሠራር እኮ ሆኖ አይደለም። ግን ይህ በዘመኑ ዘመናዊ የነበረ ቢሆንም አሁን ግን ዘመኑ ተሻግሮታል። ምንም ያህል ጥሩ ሰው ብትሆን በዚህ መዋቅር ውስጥ ከሠራህ ሥርዓቱ በራሱ ያበላሽሃል::

መንግሥት የግዥ ሥርዓቱን በብር መጠን በቀጥታና በጨረታ ማስታወቂያ የሚፈጽምበት መመሪያ አለው። ይህም ሆኖ ስላልተቻለ እንደገና ማዕከላዊ የግዥ አሠራር አምጥቷል። ቤተ ክህነት ውስጥ ግን ዝርዝር የጨረታ አሠራር፣ ዝርዝር የግዥ ሂደት አሠራር አታገኝም። ይህ ሁሉ ግንባታ እየተከናወነ ግንባታ የሚመራ መምሪያ እንኳ የላትም። የግንባታውን ጥራት የሚቆጣጠር፣ ግንባታው የሚሠራው በትክክለኛ ጨረታ ነው ወይ? የሚሠሩ ሥራዎች ከቤተ ክርስቲያኒቱ ፖሊሲዎች ጋር አብረው የሚሄዱ ናቸው ወይ? ወዘተ. ብሎ የሚያይ አካል እኮ የለም። ያም ተነስቶ ‹‹ሱቅ እከፍታለሁ›› ቢል ከልካይ የለውም፤ ‹‹ሱቅ ሳይሆን ጉልት ገበያ›› እከፍታለሁ የሚለውም ከልካይ የለውም።

ቤተ ክርስቲያኒቱ በአንዳንድ ዘርፎች ለምሳሌ በሕንጻ ግንባታ፣ በቤተሰብ ጉዳይ ወዘተ. የበርካታ ዓመታት ልምድ ባለቤት ናት። ነገር ግን ያሳየችዉ ለውጥ የለም። እነዚህ ችግሮች ሲከሰቱ የሚመለከት ሰው እንዴት ጠፋ?

በነገራችን ላይ በ1950ቹ አቡነ ቴዎፍሎስ ጀምረውት ነበር። ግን ሕንጻዎቹ ተሠርተው አልቀው ገና ቤተ ክርስቲያኒቱ ማስተዳደር ሳትጀምር ደርግ ወረሳቸው። በዚህ ምክንያት ልምዱ ሊካብት አልቻለም። አብዛኛዎቹ ሕንጻዎች ደግሞ በበጎ አድራጎት ተሠርተው የተበረከቱ ነበሩ። የተወረሱት ሕንጻዎች ሲመለሱ እነርሱን የሚያስተዳድር መምሪያ ብትከፍትም በየአጥቢያው ያሉ ሕንጻዎችን የሚያስተዳድር አካል ግን አልመደበችም። ዘመናዊውን ቤተ ክህነት ስታቋቁም የዕውቀትና የልድም ክፍተት ነበረባት። እስከአሁን ድረስ ያልተሞላው ችግር እርሱ ነዉ። ለምሳሌ አንድ በሠራተኛ አስተዳደር በቤተ ክህነት የተመደበና አንድ ደግሞ በመንግሥት በሠራተኛ አስተዳደር የተመደበ ሰው እኩል ዕውቀት የላቸውም። በመንግሥት መሥሪ ያ ቤቶች በሙያው

ልምድና ችሎታ ያለው ሰው ይቀጠራል። ቤተ ክህነት ግን እንደዚህ ያለ አሠራር የለም።

ግን እኮ የቤተ ክርስቲያን ትምህርት ቤቶች መምህራን ለመቅጠር በመስፈርት ማስታወቂያ ሲያወጡ እናያለን!

ዕውቅና ለመስጠት ትምህርት ሚኒስቴር ስለሚያስገድዳቸው ነዋ። ግን ‹‹አንድ የቤተ ክርስቲያን ትምህርት ቤት ምን መምሰል አለበት?›› ያልን እንደሆነ ‹‹ይህን የሚመልስ›› ብሎ የሚያስቀምጥ ፖሊሲ የለም። አሜሪካ ብትሄድ የካቶሊክ ትምህርት ቤቶች በደንብ ይታወቃሉ። ግልጽ የሆነ መመሪያና ፖሊሲ አላቸው። የእኛ ግን ምንም የለም። ምኑ ነው የቤተ ክርስቲያን ትምህርት ቤት ያስመሰለው? ምንም የለም። ትምህርት ሚንስቴር ይቆጣጠራቸዋል እንጅ እኮ የቤተ ክህነት ትምህርት ዘርፍ የሚባል ተቆጣጣሪ ድርጅት የላትም።

በቤተክርስቲያን ውስጥ የሙስና ጉዳይ ትልቅ መነጋገሪያ እየሆነ መጥቷል። መንፈሳዊ መሪዎችና አባቶች በዚህ ዓይነት ምግባር ተዘፍቀዉ እንዴት ነው ምዕመኑን መምራት የሚችሉት? በዚህ ይዞታቸዉ የሚያስተምሩት ሕዝብስ እንዴት ሊሰማቸዉና ሊቀበላቸዉ ይችላል?

እሱ ከባድ ነው። ምዕመኑን ከቤተ ክርስቲያኒቱ የመነጠል አደጋም አለው። ምዕመኑ አባቶቹን ማመን ያቅተዋል። ነገ አሥራት በኩራቱን ለመክፈል፣ ኑዛዜውን ለንስሀ አባቱ ለመናገር ወዘተ. ይቸግረዋል። ለዚህ ነው ቤተክርስቲያኒቱ መንቃት ያለባት። አጠቃላይ ተቋማዊ ለውጥ ያስፈልጋታል። ቤተ ክህነታዊ ለውጥ ያስፈልጋታል። መምሪያዎቿን እንደገና የማየት፣ ፖሊሲ ማርቀቅ ያስፈልጋታል። መዋቅራዊ አሠራሩ በደንብ እንደገና መፈተሽ አለበት። ጥብቅ፣ ግልጽና አሳታፊ የሆነ አሠራር መዘርጋት አለበት። ለምሳሌ አጥቢያዎች ኦዲት መደረግን መልመድ አለባቸው። በውጭ ኦዲተር ኦዲት ተደርገው መቅረብ አለባቸው። ሕዝቡ ለሰጠው ገንዘብ ጠያቂ ስለሚሆን ለሕዝቡ በግልጽ መቅረብ አለበት። ይህ አለመሆኑ ደካማ አሠራርን ተጠቅመው መቦጥቦጥ የሚፈልጉ ሰዎችን ይስባቸዋል። ጠንካራ ሥርዓት ሲኖር በዚህ መጠቀም የሚፈልጉ ሰዎች አይቀርቡም፤ ይፈሩታል።

አሁን ባለው ሁኔታ ለውጥ የሚመጣ ይመስልዎታል?

እኔ በሂደት ለውጡ በሁለት መንገድ ይመጣል ባይ ነኝ። ወይ ውስጥ ያሉት አባቶች ችግሩን በደንብ ተረድተውት ዘላቂ መፍትሔ ለመፈለግ ይነሳሉ። ካልሆነ ደግሞ ወቅቱ ያስገድዳል። እንዲህ ሆኖ መቀጠል አይቻልም። የሆነ ጊዜና ቦታ ላይ ግጭት ይፈጠራል። ግጭቱን ቀድመህ ከደረስክበትና ከፈታኸው ጥሩ ነው። ካልሆነ ግን ለውጡም ግጭቱም ይመጣል። ግን ኪሳራ ያስከትላል። ከተወሰነ ጊዜ በኋላ ትውልዱም መሸከም የማይችልበት ደረጃ ላይ ይደርሳል። ግን የዚህ ዓይነቱ ለውጥ አስጊ ነው፤ ጥሩ ለውጥ አይደለም። ለውጡ ከተቋሙ ከራሱ ቢመጣ ነው ጥሩ የሚሆነው።

ቤተ ክርስቲያኒቱ በገንዘብ እጅግ ሀብታም እንደሆነች ይታወቃል። ነገር ግን ‹‹ይህን ያህል ሀብት አላት›› ተብሎ ሪፖርት አይቀርብም። የግልጽነት አለመኖሩ ደግሞ ነገሮችን ይበልጥ እያወሳሰባቸው ነው። በእርስዎ አስተያየት ሪፖርት የማይቀርብበት ምክንያት ምንድን ነው?

እውነት ነው፤ አጠቃላይ ሀብቷን የሚመለከት ሪፖርት ቀርቦ አያውቅም። አጠቃላይ ሀብቷን ሪፖርት ለማቅረብ የሚያስችል ሥርዓትም የላትም። ይህን የሚመራ ትልቅ የፋይናንስ ተቋም ያስፈልጋል። መንግሥት እኮ ይህን ያክል ገንዘብ የሚያስተዳድረው ገንዘብ ሚንስቴር የሚባል ተቋም ይዞ ነው። ቤተ ክህነት እኮ ገንዘብ ሚኒስቴርን የሚስተካከል ትልቅ የፋይናንስ ተቋም ያስፈልጋታል። ከ35,000 በላይ አብያተ ክርስቲያናት ያሏት፣ ከ40,000 በላይ ካህናት ያሏት፣ ከ1,100 በላይ ገዳማት ያሏት ቤተ ክርስቲያን ሀብትየሚያስተዳድር ያስፈልጋታል።

የገንዘብ ተቋም ጎሰኝነቱም ሌላው የቤተ ክርስቲያን ፈተና ነው ይባላል። ይህስ እንዴት ይታያል?

እኔ ‹‹ጎሰኝነቱን የበለጠ እንዲያብብ ያደረገው የተንሰራፋው ሙስና ነው›› ነው የምለው። አካባቢያዊነት በአገራችን የኖረ ነው። ሆኖም ሙስናው ላይ ስትቆም አካባቢያዊነት ወደ ጎሳኝነትና ጠባብነት ያድጋል። ሙስና ላይ ስትቆም የምታምናቸው ሰዎችን ትፈልጋለህ። ስለዚህ ጎሰኝነቱ የቆመው ሙስናው ላይ ባይ ነኝ።

በመርህ ደረጃ ቤተ ክርስቲያን ሕንጻ ገንብታ የንግድ ተቋማትን ከማስፋፋትና ትምህርት ቤት ከማቋቋም የትኛውን ብትሠራ ተመራጭ ይሆናል?

መሆንማ የነበረበት ቤተክርስቲያን አስተማሪ ናት፤ መካሪ ናት፤ ለሕዝብ ደህንነት የቆመች ናትና የመጀመሪያ ሥራዋ አብያተ ክርስቲያናትን ማስፋፋት ነው። ቀጥሎ ትምህርት ቤቶችን መሥራት፣ የአረጋውያንን መጦሪያ መሥራት፣ የድሆችን መመገቢያ መሥራትና ሌሎችንም ማከናወን ነው የነበረባት። ‹‹እነዚህን ነገሮች ለመሥራት ገንዘብ ያስፈልገኛል›› ካለች ቀጥሎ የሚመጡ ነገሮች ናቸው። እንደምታዩት በአገራችን አብያተ ክርስቲያናቱን የንግድ ድርጅቶች ውጠዋቸዋል። ስለዚህ ድሮ ከሩቅ የምትሳለመውን አሁን ከሩቅ መሳለም አትችልም። የትኛው ነው የገዘፈ? ግዝፈት ትኩረትን ያሳያል። ቤተክርስቲያኒቱ ትንሽ ሆና የንግድ ሕንጻው ግን ግዙፍ ሆኖ ትኩረታችን የትኛው ላይ ነው? ይህ ሁሉ ቀጣዩ ትውልድ ለሚጠይቀው ጥያቄ ከባድ መልስ ነው።

The post “ቤተክርስቲያኒቱ አጠቃላይ ተቋማዊ ለውጥ ያስፈልጋታል” – ዲያቆን ዳንኤል ክብረት appeared first on Zehabesha Amharic.


ቡሩንዲ ኢትዮጵያን 2 ለ 0 አሸነፈች!

$
0
0

“ሁለት ስህተት ሰራን ሁለት ጎል ገባብን ለቀጣዮ ጨዋታ እናሻሽላለን” አሰልጣኝ ዮሀንስ ሳህሌ 

ethiopia(ኢትዮኪኮፍ) የኢትዮጵያ የቻን ብሔራዊ ቡድን 2016ቱ የቻን የማጣሪያ ጨዋታ ዛሬ ቡጁምቡራ ላይ በቡሩንዲ 2-0 ተሸንፏል። ብሔራዊ ቡድኑ ከአንድ ሳምንት በፊት አዲስ አበባ ላይ ሳኦቶሜን በአለም ዋንጫ ማጣሪያ 3-1 ማሸነፉ ይታወሳል። በዛሬው ቡድን ላይ ፕሮፌሽናሉ ሽመልስ በቀለ ብቻ ነው የሌለው እንጂ ሁሉም ተጨዋቾች ባላፈው ሳምንት ያሸነፈው ቡድን ውስጥ ነበሩ። አሰልጣኙ ሳልሀዲን በርጌቾን በዚህ ቡድን አካተው ተሸንፈዋል። ጎሎቹ ጨዋታው ሲጀመርና ጫዋታው ተጠናቆ በጭማሪ ደቂቃ ነው የተቆጠረበት። ከጨዋታው በኃላ ለስፖርት ዞን አሰልጣኝ ዮሀንስ በንዴት ተውጠው የሚከተለውን ብለዋል” ሁለት ስህተት ሰራን ሁለት ጎል ገባብን ለቀጣዮ ስህተታችንን እናሽላለን ብለዋል። የመልሱ ጨዋታ በቀጣዮ ሳምንት October 24 አዲስ አበባ ስታዲየም ይደረጋል።

The post ቡሩንዲ ኢትዮጵያን 2 ለ 0 አሸነፈች! appeared first on Zehabesha Amharic.

ከ20 ዓመት በታች የኢትዮጵያ ሴቶች ብሄራዊ ቡድን ወደ ቀጣዩ ዙር አለፈ

$
0
0

setoch
በዓለም ዋንጫ ማጣሪያ የኢትዮጵያ ከ20 ዓመት በታች የሴቶች ብሔራዊ ቡድን በአዲስ አበባ ስታዲየም ከቡርኪናፋሶ ጋር 0 ለ 0 ቢለያይም በድምር ውጤት 2 ለ 0 በማሸነፉ ወደ ቀጣዩ ዙር አለፈ።

ማጣሪያው ለ2016 በፓፓዋ ኒው ጊኒ ለምታዘጋጀው 8ኛው ከ20 ዓመት በታች የሴቶች የዓለም ዋንጫ ለማለፍ ነው።

በቡርኪናፋሶ ሙኒስፓል ስታዲየም በተደረገው ጨዋታ ኢትዮጵያ በሎዛ አበራ ባሰቆጠራቸው ሁለት ጎሎች አማካኝነት ቡርኪናፋሶን ማሸነፍ ችላለች።

ብሄራዊ ቡድኑ ባካሄዳቸው የማጣሪያ ውድድሮች እስካሁን የተቆጠሩ አራት ጎሎች በአምበልዋ ሎዛ አበራ የተገኙ ናቸው።

ኢትዮጵያ ከዚህ ቀደም ካሜሮንን ያሸነፈች ሲሆን በቀጣይ የጋና ብሄራዊ ቡድንን የምትገጥም ይሆናል።

በጎርጎሮሳዊያኑ 2016 ፓፓዋ ኒው ጊኒ በምታስተናግደው ስምንተኛው ከ20 ዓመት በታች የሴቶች የዓለም ዋንጫ አፍሪካ በሁለት አገራት ትወከላለች።

ምንጭ – ኢቢሲ

The post ከ20 ዓመት በታች የኢትዮጵያ ሴቶች ብሄራዊ ቡድን ወደ ቀጣዩ ዙር አለፈ appeared first on Zehabesha Amharic.

የአብዱ ኪያር “አልተለያየንም”ዘፈን በመንግስት ሚድያዎች እንዳይተላለፍ ታገደ

$
0
0

(ዘ-ሐበሻ) ድምፃዊ አብዱ ኪያር “አልተለያየንም” በሚል በአዲሱ የ”ጥቁር አንበሳ” ሲዲው ላይ ያቀረበው ዘፈን በመንግስታዊ ሚዲያዎች ላይ እንዳይተላለፍ ዕግድ መተላለፉን የዘ-ሐበሻ ምንጮች ከአዲስ አበባ አስታወቁ::

“በካርታ ብንለያየም – ኢትዮጵያም ኤርትራም አንድ ናቸው”… “አዲሱ ማንነቴን መቀበል አቃተኝ”… “በወላይታ ሙዚቃ ይጨፈራል በአስመራ”… የሚሉ መል ዕክቶች ያሉት በአንድነት ዙሪያ የሚያጠነጥነው ይኸው የአብዱ ኪያር ዘፈን በኢትዮጵያ ሁሉም ከተሞች ባሉ ሙዚቃ ቤቶች; በምሽት ክለቦችና መዝናኛ ቦታዎች በከፍተኛ ሁኔታ እየተደመጠ እንደሚገኝ የዘ-ሐበሻ ምንጮች ገልጸዋል::

መንግስታዊ ሚድያዎች እንዳያሰሙት የተከለከለው ይኸው “አልተለያየንም” የሚለውን ዘፈኑን ዘ-ሐበሻ እዚህ ጋብዛችኋለች:: ያድምጡት:: ለወዳጅ ዘመድዎም ያካፍሉት::


የአብዱ ኪያር “አልተለያየንም” ዘፈን በመንግስት ሚድያዎች እንዳይተላለፍ ታገደ

The post የአብዱ ኪያር “አልተለያየንም” ዘፈን በመንግስት ሚድያዎች እንዳይተላለፍ ታገደ appeared first on Zehabesha Amharic.

በስደት የሚገኘው የመምህራን ማህበር መግለጫ አወጣ –“የኢትዮጵያ መምህራን ሰቀቀን ይብቃ”

$
0
0

ethiopian teachers
ኦክቶበር 5 የዓለም መምህራን ቀን የኢትዮጵያ መምህራን ዕለቱን ያሰቡት በሰቀቀን!
ጥቅምት 5 ቀን 2008ዓ.ም

Teachers Unionአገሮች ስለመምህራንና የትምህርት ጉዳይ እያነሱ መነጋገር ከጀመሩበት ወቅት የኦክቶበር 5/1966 በፈረንሳይ -ፓሪስ ከተማ የተካሄደው ኮንፍረንስ በታሪካዊነቱ የሚጠቀስ ነው። ከዚያ ወቅት በኋላ ቆየት ብሎ ኦክቶበር 5 ቀን 1994 የመጀመሪያው የዓለም መምህራን ቀን ተመሰረተ።ከዚያን ጊዜ ጀምሮ በያመቱ መምህራንና ማህበሮቻቸውን በመዘከር ኦክቶበር 5 የዓለም መምህራን ቀን በመባል ይታወሳል። ከዚሁ ጋር ተያይዞ የማስተማር ሙያ ክብርና ተቀባይነት እንዲያገኝ በኦክቶበር 12/ 1997 በ29ነኛው የተባበሩት መንግስታት የትምህርት ፣ የሳይንስና ባሕል ድርጅት (UNESCO) ጠቅላላ ጉባኤ ( ኮንፍረንስ) ሲከፈት በታደሙት የዚሁ ድርጅትና የዓለም ሰራተኞች ማህበር ( ILO= International Labor Organization) ተወካዮች ስምምነት ላይ ተደርሶ በፊርማ ጸድቋል። የመምህራን ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ የማህበሩ ዓላማና ፋይዳው መምህራን ለቀጣዩ ትውልድ መሰረታዊ ፍላጎቶችና ፣ ባጠቃላይ ለህብረተሰቡ ዕድገት አጥጋቢ ውጤት እንዲያስመዘግቡ ለመርዳት ነው። ስለሆነም ዩኔስኮ የዓለም መምህራን ቀን የመክበር ግንዘቤ የሚላከው መምህራን ለትምህርትና ለሁለንተናዊ ዕድገት በሚያበረክቱት ፍሬያማ ተግባር ከመሆኑ አንፃር እንደሆነ ያምናል።

Read full story in PDF

The post በስደት የሚገኘው የመምህራን ማህበር መግለጫ አወጣ – “የኢትዮጵያ መምህራን ሰቀቀን ይብቃ” appeared first on Zehabesha Amharic.

የአርበኞች ግንቦት 7 ሪከርድ የሰበረ የገቢ ማሰባሰቢያ ዝግጅት በሚኒሶታ * ነአምን ዘለቀ አርበኞች ግንቦት 7 መንፈስ ነው አሉ (ሪፖርታዥ)

$
0
0

“የኤርትራ መንግስት ከራሷ ጋር የታረቀች ጠንካራ ኢትዮጵያ እንድትመሰረት ይፈልጋል”

“ሁሉንም ፖለቲካ ሃይሎች ያካተተ የሽግግር ሂደት ይኖራል”

“የወደብ ጥያቄን በተመለከተም ወደፊት በድርድር/በሰጥቶ መቀበል የሚፈታ ይሆናል እንጂ አሁን የትግሉ አጀንዳ መሆን የለበትም”

“የመረጃ ትንሽ የለውም… መረጃ አይናቅም” 

 

(ዘ-ሐበሻ) በሚኒሶታ ትናንት ማምሻውን ለአርበኞች ግንቦት 7 ገቢ ማሰባሰቢያ የተደረገው ዝግጅት በታሪካዊነቱ እንደሚቀመጥ የሚኒሶታ ነዋሪዎች አስታወቁ:: በሚኒሶታ ታሪክ ለአንድ የፖለቲካ ድርጅት በአንድ ቀን 78 ሺህ ዶላር በላይ ሲሰበሰብ የትናንቱ የመጀመሪያው ነበር::

neamin zeleke

ከ200 በላይ ሃገር ወዳድ ኢትዮጵያውያን በተሰባሰቡበት በዚሁ ታሪካዊ የአርበኞች ግንቦት 7 የገቢ ማሰባሰብ ዝግጅት ላይ በክብር እንግድነት የተገኙት አቶ ነአምን ዘለቀ እና ወጣት ሚካኤል ከላስቬጋስ ነበሩ:: ይህ የገቢ ማሰባሰብ ዝግጅት የተከፈተው የንቅናቄው ሊቀመንበር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋና አቶ ኤፍሬም ማዴቦ ከአስመራ በቭዲዮ ባስተላለፉት መልዕክት ነበር::

 

ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በመልዕክታቸው እየተደረገ ያለው ትግል አንድን አምባገነን ጥሎ ሌላ አምባገንን ለመተካት ሳይሆን የተሻለች ዴሞክራሲያዊት ኢትዮጵያን ለመመስረት እንደሆነ አስምረውበታል:: ከሌሎች የፖለቲካ ፓርቲዎች ጋርም በኢትዮጵያ አንድነት በመተማመን በመነጋገር ላይ መሆናቸውን እና ጥሩ ነገር እንደሚሰማም የገለጹት ፕሮፌሰሩ በቶሎ ትግሉ እንደሚጀመር አስታውቀዋል::

በዕለቱ በአዳራሹ በክብር እንግድነት የተገኙት የንቅናቄው የውጭ ጉዳይ ሃላፊ አቶ ነአምን ዘለቀ ባሰሙት ንግግር “አርበኞች ግንቦት 7 መንፈስ ነው” ብለዋል:: ይህን ሲያብራሩም “የአርበኞች ግንቦት 7 ተዋናዩም ተመልካቹም ሕዝቡ ነው:: ንቅናቄው ዘረኝነትን በተንገሸገሸ – እኩልነት; ፍትህ እና ሰላም በተጠማው የኢትዮጵያ ተማሪ… ወጣት… ገበሬ.. ሴት… ወንድ ውስጥ ያለ ሕዝባዊ ትግል ነው:: ይህም ማለት በሁሉም የህብረተሰብ ክፍል ውስጥ ንቅናቄው አለ ማለት ነው:: ይህ መንፈስ ሥር እየሰደደ ሄዷል:: አሁን ባለው ዘረኛው ስርዓት ብዙዎች ተገድለዋል… በግፍ ታስረዋል በሚሊዮን የሚቆጠሩ ተንገላተዋል:: እነዚህ ሁሉ ሚሊዮኖች በውስጣቸው የአርበኞች ግንቦት 7 መንፈስ አላቸው::”

አቶ ነአምን ንግግራቸውን ቀጥለው “የወያኔ ፋሽስታዊ አገዛዝ በግፍ ብዙዎችን ከመሬታቸው ፎቅ ካልሰራችሁ እየተባሉ እንዲገፉ አድርጓል:: ቦታቸው ተቸብችቧል:: እነዚህ ዜጎች መሥእረታዊ የዜግነት መብታቸውን ተነጥቀዋል:: በጋምቤላ በደቡብ እየተደረገ ያለው ይኸው ነው:: የዘር ማጥፋት እየደረሰባቸው ነው:: እነዚህ የወያኔ ሰለባ የሆኑ ወገኖቻቸን ዴሞክራሲን የሚናፍቁ ናቸው:: ብዙ ኢትዮጵያውያን ካለፍርድ በ እስር ይማቅቃሉ:: ፍርደ ገምድሉ ሥር ዓት በፍትህ ላይ ቀልደዋል:: በነዚህ ሚሊዮኖች ውስጥ ሁሉ የአርበኞች ግንቦት 7 መንፈስ አለ” ብለዋል::

“በኮንትሮባንድና በዘረፋ የተሰማሮ 90% የሕወሓት ጀነራሎች እና መኮንኖች ሃብታም በሆኑበት መከላከያ ሠራዊት ውስጥ… አርበኞች ግንቦት 7 አለ:: ሠራዊቱ በከንቱ የወያኔ ጣልቃ ገብነትና ወረራ ደማቸው ደመከልብ ለመሆን ችሏል:: ይህ ሠራዊት እኩልነትን የተጠማ ሠራዊት ነው::” በማለት አሁን ስላለው የሕወሓት/ኢሕ አዴግ ሠራዊት ስለሚደርስበት የዘር መድልዎ የጠቀሱት አቶ ነአምን የትግሉ መዳረሻ የት ነው? በሚለው ንግግራቸው አርበኞች ግንቦት 7 መዳረሻ ዴሞክራሲያዊ ሥር ዓት መገንባት እንደሆነ ገልጸዋል:: አሁን ያለው ሥርዓትም በኃይል የወጣ የመጨረሻው አምባገነን ሥርዓአት ይሆናል ብለዋል::

“ሁሉንም ፖለቲካ ሃይሎች ያካተተ የሽግግር ሂደት ይኖራል:: ከሁሉም ባለድርሻዎች ጋር ቁጭ ብለን የምንነጋገርበት ጊዜ ሩቅ አይሆንም” ያሉት አቶ ነአምን በ3ኛ ደረሻ ስለ ኤርትራ መንግስት አብራርተዋል::

“የኤርትራ መንግስት ከራሷ ጋር የታረቀች ጠንካራ ኢትዮጵያ እንድትመሰረት ይፈልጋል:: እንድትበታተን ይሰራል ብለን አናምንም:: ኢትዮጵያን የማዳከም ስልት ወይም ፖሊሲ ኤርትራ አላት ብለን አናምንም:: በጣም ጤናማ ስኬታማ ኢትዮጵያ እንድትኖር የኤርትራ መንግስት እንደሚፈልግ ነው የምናውቀው” በማለት የተናገሩት አቶ ነአምን አርበኞች ግንቦት 7 ከኤርትራ መንግስት ጋር ኢትዮጵያን በሚመለከት ስትራቴጂካዊ በሆኑ ጉዳዮች; በወደብ ጥያቄ ለመደራደር ምንም ዓይነት ስልጣን እንደሌለው እንዲሰመርበት እፈልጋለሁ ብለዋል::

namin ze

“የወደብ ጥያቄን በተመለከተም ወደፊት በድርድር/በሰጥቶ መቀበል የሚፈታ ይሆናል እንጂ አሁን የትግሉ አጀንዳ መሆን የለበትም” ያሉት አቶ ነአምን በ4ኛ ደረጃ በውጭ ከሚገኘው ኢትዮጵያዊ ይህ የነፃነት ትግል ምን እንደሚጠብቅ አብራርተዋል:: በውጭ ያለው ኢትዮጵያዊ ይህን ትግል በዲፕሎማሲው; በቁሳቁስ እና በገንዘብ ሊደግፍ እንደሚገባ ያስታወቁት የንቅናቄው የውጭ ጉዳይ ኃላፊ “በውጭ ያለው ኃይል በየከተማው ያሉትን ሴናተሮችን እና ኮንገረሶችን ስለኢትዮጵያ መንግስት ጥፋቶች ሊነግሩ ይገባል:: በየከተማው ባሉ ሚዲያዎች እየወጡ በመጻፍና በመናገር የዲፖሎማሲው አካል በመሆን ትግሉን ማገዝ ይገባቸዋል:: የህክምና ሙያ ላይ የተሰማሩ ሰዎችም እንዲሁ በመድሃኒት አቅርቦት ላይ ብዙ ይጠበቅባቸዋል” ያሉት አቶ ነአምን አርበኞች ግንቦት 7 ጠላትን በተመለከተ ትልቅ የመረጃ ማሰባሰቢያ ኔትወርክ እንዳለው ጠቁመው ሁሉም ኢትዮጵያዊ መረጃዎችን ለድርጅቱ በተዘራጋው መዋቅር በኩል እንዲያስተላለፍ ጠይቀዋል:: “የመረጃ ትንሽ የለውም… መረጃ አይናቅም” ያሉት አቶ ነአምን በውጭ ያለው ኢትዮጵያዊ በስር ዓቱ ላይ እስካሁን እያሳየ ያለውን ሕዝባዊ እምቢተኝነት እንዲቀጥል አበክረው ጠይቀዋል::

ከነመሪዎቹ አስመራ ለሚገኘው አርበኞች ግንቦት 7 መርጃ የተደረገው ጨረታ ላይ የግንባሩ ሴት ታጋዮች ምስል ቀርቦ 20 ዶላር ከተሸጠ በኋላ ወደ ጥያቄና መልስ ተገብቷል::

ፖስትሮድ የሚገኙ የኤርፖርት ታክሲ ሾፌሮች 10 ሺህ ዶላር አዋጥተው ሰጥተዋል::

በስፍራው “የፈራ ይመለስ” የሚል ቲሸርትና ህፃናትን ሳይቀር ያሳተፈ የገንዘብ ልገዛ ለግንባሩ ተደርጓል::

ከተሰብሳቢውም በአሁኑ ወቅት የሕወሓት/ኢህአዴግ መንግስት በሃይማኖቶች ውስጥ ጣልቃ በመግባት በተለይ ተሃድሶ የሚባል ነገር በኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤ/ክ በመፍጠር ሕዝቡን ለማለያየት አውቆ እየሠራ መሆኑን አርበኞች ግንቦት 7 እንዴት እንደሚመለከተው; ሞላ አስገዶም የትህዴን ሠራዊቱን ይዞ ወደ ወያኔ ሲገባ ከግንባሩ በቂ ምላሽ አልተሰጠም የሚል; አቶ ነአምን በቭኦኤ ላይ ቀርበው ስለአሜሪካዊ ዜግነት እንዳላቸው ሲጠየቁ ለምን መመለስ እንዳልፈለጉና ተመሳሳይ ጥያቄዎች ቀርበውላቸዋል::

አቶ ነአምን አሁንም የአሜሪካዊ ዜጋ ስለመሆናቸውና ስላለመሆናቸው መናገር እንደማይፈልጉ ገልጸዋል:: ይልቁንም በቅርብ ጊዜ የሕወሓት አስተዳደር “የአርበኞች ግንቦት 7 አመራሮች የአሜሪካ ዜግነት ያላቸው ስለሆኑ እንከሳቸዋለን” ማለቱን ጠቅሰው “ይምጣና ይሞክረን:: እንደውም ክስ ቢመሰርቱብን ጥሩ ነው:: በክሱ ሂደት ምን ዓይነት ወንጀሎችን እንደሰሩ እናሳያቸዋለን” ብለዋል:: አቶ ነአምን አክለውም የሰሞኑ የወያኔ ድንፋታ የአሜሪካንን ሕግ ካለማወቅ የመጣ መሆኑን አስምረውበታል::

በሞላ አስገዶም ዙሪያ ለሕወሓት መንግስት በቂ የሆነ ምላሽ አልተሰጠበትም ለሚለው ጥያቄም “በቂ ምላሽ ስለሰጠንበት እኮ ነው ዛሬ ይህን ሁሉ አዳራሽ ሙሉ ሰው ያያችሁት” ሲሉ መልሰዋል::

የአርበኞች ግንቦት 7 የገቢ ማሰባሰብ በተለይም የአቶ ነአምን ዘለቀ ንግግርን ማንኛውም ጋዜጠኛ እንዳይቀርጽ መከልከሉ ተሰብሳቢውን አሳዝኗል:: በተለይ አርበኞች ግንቦት 7 ለመናገር ነፃነት እታገላለሁ የሚል ድርጅት በመሆኑ እንዲህ ያለው የጋዜጠኛ ክልከላ ገና ከጅምሩ እንዲህ ከሆነ የወደፊቱ ያሳስበናል የሚሉ አስተያየቶችም ተደምጠዋል:: በአጠቃላይ ግን አርበኞች ግንቦት 7 በሚኒሶታ የተሳካ ገቢ ማሰባሰብ ማድረጉን በሙሉ አፍ መመስከር ይቻላል::

The post የአርበኞች ግንቦት 7 ሪከርድ የሰበረ የገቢ ማሰባሰቢያ ዝግጅት በሚኒሶታ * ነአምን ዘለቀ አርበኞች ግንቦት 7 መንፈስ ነው አሉ (ሪፖርታዥ) appeared first on Zehabesha Amharic.

Health: ብዙ እያደረግን ክብደት የማንቀንስባቸው 10 ምክንያቶችና መፍትሄዎቻቸው!

$
0
0

lose waight

ከኤሊያና ሔኖክ

ብዙ ቢያደርግም ከልክ ካለፈው ነየሚያወጣው መፍትሄ በማጣቱ የተቸገረ ወዳጅ አለኝ የምግብ ፍላጎቱ ከብዙዎቻችን የተለየ አይደለም ያገኘውን ለመብላት አፒታይቱ የሚከለክለው ወጣት ባይሆንም ቀጭን የሚባል ወጣት ነው፡፡ በዚህ ደስተኛ አይደለም፡፡ ያወፍሩኛል ብሎ የሚያስባቸውን አማራጮች በሙሉ ከመጠቀም ወደኋላ አይልም፡፡ ከጥሬ የበሬ ሥጋ እስከ አሳማ ሥጋ ይመገባል፡፡ እንዲሁም በሐኪሞች የታዘዘለትንና በገበያ ላይ ያሉትን መድሃኒቶች ከውጪም ከሀገር ውስጥ አፈላልጎ ይውጣል፡፡ ነገር ግን አሁን ላይ የሚፈልገውን ለውጥ እያገኘ ባለመሆኑ ሁሉንም ነገር እርግፍ አድርጎ ወደ መተው እየመጣ ነው፡፡ ጉዳዩ በመቀጠል ከሚቀርበው ሃሳብ ጋር በቀጥታ አይገናኝም፡፡ የችግሩ ባህሪ ግን ተመሳሳይ ይመስላል፡፡

ምግብ ወዳጆችን ጨምሮ ለአንዳንዶች ክብደት መቀነስ በፈለጉት የጊዜ ገደብ እና ሁኔታ ውስጥ እንኳን በቀላሉ የሚሳካላቸው ተግባር ሲሂን ለሌሎቻችን ደግሞ ተግባሩ (ክብደት ቅነሳው) ዋናው የህይወታችን ተግባር አድርገነው እንኳን በመጨረሻ የምናወራርደው ሂሳብ እኛን የሚጠቅም አይሆንም፡፡ ለቁመታችን ሲካፈል ያልተመጣነውን ክብደትን ለመቀነስ ስፖርታዊ እንቅስቃሴ አመጋገብን መለየት እና ሌሎች አማራጮችን በመጠቀም ላይ ነዎት፡፡ ነገር ግን የሚፈለገውን ለውጥም ሆነ ፍንጭ አላዩም እንበል ቀጣዩ እርምጃዎ ምን ሊሆን ይችላል? እንደ ቀጭኑ ወዳጄ በተስፋ መቁጥ ሁሉንም ነገር ይተዉት ይሆን? ሁላችንንም ሊያሳምን የሚችለው ተስፋ መቁረጥ መፍትሄ ሆኖ አለማወቁን ነው፡፡ በጤና እና በደስታ ላይ ተስፋ ተቆርጦ ወዴት ይደርሳል፡፡

ሙዳ ሥጋ ከሰውነታችን ላይ ለመቀነስ የያዝነውን እቅድ ከግብ ላለማድረስ ምክንያት የሚሆኑ በርካታ ጉዳዮች ይገጥመናል፡፡ ለዚህ መሰረታዊ መፍትሄ ተደርጎ የሚወሰደው ሁሉንም ችግሮች ልንቋቋማቸው የምንችለው እንደ ሳይንቲስቶች መጋፈጥ ስንችል መሆኑ ነው፡፡ ሌላው በራስ ላይ ጥናት ማድረግ ነው፡፡ በየጊዜው የሚታዩ ለውጦችን በበመዝገብ ደግሞ ተስማሚዎቹን መፍትሄዎች ለመለየት ይጠቅማል፡፡

ክብደት ለመቀነስ ብዙ ብናደርግ ለውጥ የማናይበት ምክንያት ምንድን ነው? እስር የተጠኑ ምክንያቶችና መፍትሄዎችን እንቃኝ፡፡

1. ሥራችን ወይም ኑሯችን እንዳንቀሳቀስ ሲያደርገን

የብዙዎቻችን የክብደት ቅነሳ እቅድ የሚከሽፉበት ዋነኛው ምክንያት ነው፡፡ በተለይ ለዓመታት ህይወታቸውን በዚህ መንገድ የሚኖሩ ግለሰቦች ጠዋትና ማታ የስፖርት መስሪያ ማዕከላትን ቢጎበኙም የክብደት ቅነሳ ሂደቱ ውጤታማ ላይሆን ይችላል፡፡ ተጨማሪ እንቅስቃሴ ሰዓት በመውሰድ አይደለም ወደ መፍትሄው የምንመጣው፡፡ በወንበር ላይ እና በኮምፒዩተር ፊት ረዥሙን ሰዓት የምናሳልፍ ከሆነ በተቻለ መጠን በቀን ውስጥ 10 ኪሎ ሜትር የሚሸፍን ርቀት በእርምጃችን መሸፈን የምችልበትን ዕድል መፍጠር ከቻልን ሳናውቀው ከፍተኛ መጠን ያለውን ካሎሪ እንድንቀንስ ይረዳናል፡፡

2. ያለገደብ እንቅስቃሴ መስራት፡-

አንድ ጀንበር ለውጥ ማምጣትን ሰንቀው ወደ ስፖርት ማዕከላት የሚመጡ ሰዎች ድካማቸው ጊዜ እና ትዕግስታቸውን ሊያሰጣቸው ቢችል እንጂ ለውጡ አመርቂ ላይሆን ይችላል፡፡  እንቅስቃሴ ውጤታማ የክብደት መቀነሻ መሳሪያ የመሆኑን ያህልረሃብ ጠሪ ነው፡፡ እንቅስቃሴው ልክ ባጣ መጠን ሰውነታችን የሚጠይቀን ምግብም መጨመሩ የሚጠበቅ ነው፡፡ አፒታይትን መቆጣጠር ያለገደብ ስፖርትን ለሚያዘወትሩ ሰዎች ከባዱ ችግር ይሆናል፡፡ ባለሙያዎች እነዚህ አካላት በተቻለ መጠን ከመደበኛው እንቅስቃሴ ባሻገር በ10-15 ኪሎ ሜትር ርቀት እንዲገድቡ ይመክራሉ፡፡ በመሰረታዊነት ደግሞ ስፖርትን እንደ ሥራ ሳ ይሆን በተዝናኖት መንገድ ማከናወኑ ጠቃሚ ነው ይላሉ፡፡

3. ምግብን በሚገባ አለማኘክ

በዝግታ አለመመገብ፣ አነስተኛ መጠን ያለውን ምግብ ወደ ሰውነት ለማስገባት አለመምረጥ እና ምግብን አለማጣጣም የክብደት ቅነሳ እቅድን የሚፈትኑ ተብለው የተለዩ ናቸው፡፡ እርግጥ ነው እነዚህን ልማዶች ማስተካከል የኑሯችን አካል ማድረግ ከባድ ጉዳይ ነው፡፡ ይሄን ልምድ ለማዳበር በተቻለ መጠን የጎረስነውን ስናኝክ ለመቁጠር መሞከር እና ድግግሞሹን ከፍ ማድረገት አንዱ መንገድ ነው፡፡የምንመገበው እንድናውቅ፣ እንዳናጣጥም እንዲሁም እንድንመጥን ሂደቱ ይረዳናል፡፡

4. በቂ እንቅልፍ አለማግኘት

አዕምሮአችን እና ሰውነታችን ስንምገብ እና ስንተኛ በሚንቀሳቀሱ የተለያዩ ሆርሞኖች ላይ ጥገኛ ነው፡፡ መደበኛው ኡደት ታዲያ ከተመገብን በኋላ በተመሳሳይ ቀን ከበቂ እንቅልፍ በኋላ ልንነቃ እንደሚገባ ያዘናል፡፡ ስለዚህ ትንሽ መተኛት ወይም እንልፍ ማጣት በቀጥታ ውፍረት ከመጨመር ጋር ይገናኛል፡፡ በቀን ውስጥ የህይወት ውጣ ውረዳችንን ከፈፀምን በኋላ መተኛት ቅድሚያ የምንሰጠው ጉዳይ መሆን አለበት፡፡

5. በተለያዩ መንገዶች ያቃጠልናቸውን ካሎሪዎች መልሰን መተካት

የስፖርት እንቅስቃሴ ስናደርግ ተጨማሪ ካሎሪዎችን እንድናቃጥል ዕድል ይኖረናል፡፡ ለዛም ነው እንቅስቃሴ እጅግ ውጤታማ የክብደት መቀነሻ መንገድ ሆኖ የሚወስደው፡፡ ነገር ግን አንዳንዶች ለለውጠ የተጋነነ ግምት ይሰጣሉ፡፡ ወይም እንቅስቃሴ ማድረግ ብቻውን በቂ እንደሆነ ያስባሉ፡፡ ‹‹ዛሬ ስፖርት ሰርቻለሁ ከአሁን በኋላ ምን ይመጣብኛል›› ሲሉ የሚያስቡም አይጠፉም፡፡ ስለዚህ ሆዳቸው በጠየቃቸው መጠን እና ከአቅም በላይ ይመገባሉ፣ ይጠጣሉ፡፡ እንቅስቃሴ ሊጠቅመን የሚችለው በትክክል ተጨማሪ ስቦችን ለመቀነስ ሲሆን እንጂ ተጨማሪ እንድንመገብ ወይም አፒታይታችንን ጥሩ አድርጎ እንዲከፍትን ሲሆን አይደለም፡፡

6. እንቅስቀሴ ላይ ብቻጥገኛ መሆን

እንቅስቃሴ ከየሰውነታችን አላስፈላጊ ካሎሪ እና ስብን በማስወገድ የተስተካከለና ጤናማ ሰውነት እንደሚያላብሰን ነጋሪ የማያስፈልገው ሀቅ ነው፡፡ ነገር ግን ሌላም እውነታ አለ፡፡ እንቅስቃሴ ብቻውን በምንፈልገው መጠን ክብደት ለመቀነስ አያስችለንም፡፡ ብዙ መቶዎችን ወይም በሺ የሚቆጠሩ ካሎሪዎችን በደቂቃ ልዩነት ብቻ መብላት ከምንችልበት ሁኔታ አንፃር በአንድ ጠንካራ እንቅስቃሴ ማስወገድ የምንችለው 400 እና 500 ካሎሪ ከፍተኛ ለውጥ ነው ማለት ላይሆን ይችላል፡፡ አመጋገባችንን ማስተካከል ካልቻልን እና በምንወስደው የካሎሪ ብዛት ላይ ገደብ ካላበጀን የጀመርነው ስፖርት ውሃ ቅዳ ውሃ መልስ ሊሆን ነው ማለት ነው፡፡

7. እንደምናስበው ጤናማ ምግቦችን እየተጠቀምን አይደለም

አደግን የሚሉት ሀገራት የአመጋገብ ባህል ቀሪውን ዓለም በሂደት እየተቆጣጠረው ይገኛል፡፡ በርካታ የዓለማችን ህዝብ ከውፍረት ችግር ጋር ለመኖሩ እንደ ምክንያት የሚቀመጡትም እነዚህ ምግቦች ናቸው፡፡ ሰዎች በመጥፎ ሁኔታ ጤናማ ያልሆኑ ምግቦችን ስለመጠቀማቸው እንኳን እርግጠኞች አይደሉም፡፡ ወይም ችግር ውስጥ ስለመሆናቸው ምንም አያውቁም፡፡

8. ቁርጠኛ አለመሆን

ለእንቅስቃሴ ፕሮግራሞቻችንን እና አመጋገባችን ላይ ያደረግነውን ማዕቀብ አክብረን ብንመጣም እስከ መጨረሻው የመዝለቅ ተፅዕኖ ውስጥ ስንወድቅ የሚመጣ ነው፡፡ ወይም እቅዳችንን በጀርመንበት ፍጥነት እና ተነሳሽነት ማስጓዝ አለመቻልም የቁርጠንነታችን ውስንነት መገለጫ ነው፡፡ መፍትሄውም በእቅዳችን ዙሪያ ወጥነትን ማሳየት እና ለእንቅፋቶች በቀላሉ አለመሸነፍ ይሆናል፡፡

9. የተሳሳቱ እንቅስቃሴዎችን ማድረግ

በቅድሚያ ወደ እንቅስቃሴ ስንገባ ባለሙያዎችን ማማከር መሰረታዊው ጉዳይ ነው፡፡ በየትኛው የሰውነታችን ክፍል ላይ በማተኮር

መደበኛውን የስፖርት ክፍለ ጊዜ መጨረስ እንዳለብን ማወቅ ይጠበቅብናል፡፡ የብዙዎች ችግርም ይሄንን ቅድመ ሁኔታ አለማወቅ ሲሆን ያሰቡትን ውጤት ሳያገኙ ሲቀሩም ወደ ተስፋ መቁረጥ ይመራቸዋል፡፡ ስለዚህ አንዱ መድሃኒት ከተሰራለት ውጪ ለሌላ በሽ እንደማይፈይድ ሁሉ ሁሉም እንቅስቃሴዎች በእኩል መጠን ለውፍረት ችግራችን መፍትሄ ላይሰጡን ይችላሉ፡፡ ስለዚህ በቅድሚያ እቅድ ስንነድፍ ይሄንን መሰረታዊ ጉዳይ መለየት ይኖርብናል፡፡

10. በተፈጥሮ ኢንሱሊን ተከላካይ መሆን

ጤናማ አመጋገብን እየተከላችሁ ነው እንበል፡፡ ነገር ግን በዚህ ሂደት ማሳካት የሚገባችሁን ያህል ክብደት አልቀነሳችሁም፡፡ ምክንያቱ ምን አልባት ሰውነታችሁ ኢንሱሊን ተከላካይ በመሆኑ የሚመጣ እክል ሊሆን ይችላል፡፡ ኢንሱሊን ተከላካይ ስንሆን ሰውነታችን ካሎሪዎችን ከማቃጠል ይልቅ ወደ ስብነት የመቀየር ዕድሉ ሰፊ ይሆናል፡፡ ይሄም ማለት ከሌላ ሰው እኩል መጠን ያለው እና ተመሳሳይ ምግብ እየተመገብን ቢሆንም ተጨማሪ ክብደት የማካበት ዕድል ይኖረናል፡፡ መልካሙ ዜና በተፈጥሮ ኢንሱሊን ተከላካይነት ችግርን ዝቅተኛ የካርቦን ሃይድሬት ክምችት ያላቸውን ምግቦች በመጠቀም ማስተካከል መቻሉ ነው፡፡ ከ2-8 ሳምንታት ድረስ በዚህ አመጋገብ ውስጥ መቆየት ኢንሱሊን ወሳጅነታችንን ሊያሳድግልን እንደሚችል ባለሙያዎች ያስረዳሉ፡፡

The post Health: ብዙ እያደረግን ክብደት የማንቀንስባቸው 10 ምክንያቶችና መፍትሄዎቻቸው! appeared first on Zehabesha Amharic.

በጎጃም ክ/ሀገር ደብረማርቆስ የደርግ ቀይ ሽብር ተሳታፊ የነበረው አረመኔ የደርግ አባል ፻ አለቃ እሸቱ ዓለሙ በቁጥጥር ሥር ዋለ

$
0
0

Yat weld
ከ«ያ ትውልድ ተቋም» የተሰጠ ጋዜጣዊ መግለጫ

የከበረ ሰላምታችንን በቅድሚያ እያቀረብን፤
ደም ያዘለ ዶሴ፤ ልዩ አቃቤ ሕግ ጽ/ቤት ዘገባ ጥር 2002 ዓ.ም. አዲስ አበባ።
ከአገኘነው የ፻ አለቃ እሸቱ ዓለሙ የወንጀል ዘገባ የቀነጨብነውን በማቅረብ እንጀምራለን

Read full story in PDF

The post በጎጃም ክ/ሀገር ደብረማርቆስ የደርግ ቀይ ሽብር ተሳታፊ የነበረው አረመኔ የደርግ አባል ፻ አለቃ እሸቱ ዓለሙ በቁጥጥር ሥር ዋለ appeared first on Zehabesha Amharic.


Hiber Radio: የኢትዮጵያው አገዛዝ ሶማሊያ ውስጥ የሚዋጋው በአሜሪካ ግፊት መሆኑን ወታደራዊ ሰነድ አጋለጠ * የኢትዮጵያው አገዛዝ የውጪ ምንዛሪ ዕጥረት አጋጥሞታል * የኦባንግ ሜቶ ቃለምልልስ

$
0
0

Hiber Radio
የህብር ሬዲዮ ጥቅምት 7 ቀን 2008 ፕሮግራም

<...> አቶ ነአምን ዘለቀ የአርበኞች ግንቦት ሰባት የውጭ ግንኙነት ሀላፊ በሚኒሶት በተደረገው የግንባሩ ሕዝባዊ ስብሰባ ላይ ለተጠየቁት ከሰጡት ምላሽ(ቀሪውን ያዳምጡት)

አቶ ኦባንግ ሜቶ የትብብር ለአዲሲቷ ኢትዮጵያ ዳይሬክተር በወቅታዊ ጉዳይ ላይ ከሰጡት አስተያየት (ሙሉውን ያዳምጡት)

እስራኤልና ፍልስጤምን ሰሞኑን ደም ያቃባው የጎዳና ላይ ግጭት እና የዓለም አቀፉ ማህበረሰብ ስጋት እና ቁጣ ሲዳሰስ (ልዩ ጥንቅር)

ሌሎችም

ዜናዎቻችን

የኢትዮጵያው አገዛዝ ሶማሊያ ውስጥ የሚዋጋው በአሜሪካ ግፊት መሆኑን ወታደራዊ ሰነድ አጋለጠ

በሚኒሶታ ለአርበኞች ግንቦት ሰባት የጀመረውን ትግል ለማጠናከር አገር ወዳድ ኢትዮጵያውያን 78 ሺህ ዶላር አዋጡ

በኢትዮጵያ ያለው አገዛዝ ኢኮኖሚው ውድቀት ላይ መሆኑን አመነ

የውጪ ምንዛሪ ዕጥረት አጋጥሞታል

በቀይ ሽብር ጊዜ ፈጽመዋል በተባለው ወንጀል ተጠርጥረው በኔዘርላንድ በቁጥጥር ስር የዋሉት ኢትዮጵያዊ በአገር ቤት ሞት ተፈርዶባቸዋል

አምንስቲ ኢንተርናሽናል የዞን 9 ጦማሪያን አስቀድሞም መታሰር እንዳልነበረባቸው ገለጸ

የድምጻዊ አብዱ ኪያር አዲሱ > ዜማ በአገዛዙ ሚዲያዎች እንዳይደመጥ ታገደ

የቦስትዋና ከፍተኛ ፍ/ርድ ቤት ለአስር ኤርትራውያን እግር ኳስ ተጫዋቾች የፖለቲካ ጥገኝነት ሰጠ

ሌሎችም ዜናዎች አሉ

The post Hiber Radio: የኢትዮጵያው አገዛዝ ሶማሊያ ውስጥ የሚዋጋው በአሜሪካ ግፊት መሆኑን ወታደራዊ ሰነድ አጋለጠ * የኢትዮጵያው አገዛዝ የውጪ ምንዛሪ ዕጥረት አጋጥሞታል * የኦባንግ ሜቶ ቃለምልልስ appeared first on Zehabesha Amharic.

ሞላ አስገዶም –ድከሚ ያላት ጥቁር ሴት እጇን ትነቀሳለች

$
0
0

Molla Asgdom 3
(ሰለሞን ከኖርዌይ በርገን)

የሞላ አስገዶም ነገር

ሠውየውን በቴሌቭዥን መስኮት ላይ ግስጥ ብሎ እና በበርካታ የዘመኑ አድርባይ ጋዜጠኞች ተከብቦ ስመለከተው ምን ይቀባጥር ይሆን ብዬ ለመስማት ጆሮዬን አቀናሁ፡፡ ሞላ አስገዶምም ጉሮሮውን ጠራርጎ ፍፁም ግራ በተጋባ እና ባልተረጋጋ መንፈስ መናገር ጀመረ፡፡ ሰውዬው ገና አንድ ዓረፍተ ነገር ሳይጨርስ ውሃ ጠማው፤ እኔም ይሔን አስከፊ ስርዓት በኃይል እንጥላለን ብለው ሊታገሉ በረሃ ለወረዱት ታጋዮች ወዴት እንደሚሔድ ሳይነግራቸው ወያኔ ለሚባል አውሬ አሳልፈህ ሰጥተህ ጭዳ ያደረግካቸው ንፁኃን ደም ገና ብዙ ያደርስካል፤ እንኳን ውሃ ጥም እያልኩኝ በሆዴ ማዳመጤን ቀጠልኩ፡፡ ሰውዬው ምንም ነውር የሚያውቅ አልመሰለኝም፤ ልክ እንደ ህፃን ልጅ አፉን በልብሱ ሲጠርግ፣ ብዙም ሳይቆይ የሚናገረው ሲጠፋው፣ አፍንጫውን ማሸት ይባስ ብሎ ፀጉሩን ማከክ ቀጠለ፡፡ ሰው ለካ ሞገሱ ክብሩ ነው; እውነት ሲርቀው ጥላቢስ ይሆናል የሚባለው አባባል፣ አባባል ብቻ እንዳልሆነ በሞላ አስገዶም አየሁት አልኩኝ፡፡ ሰውዬው መቀባጠሩን ቀጠለ፤ “በዚህ ደረጃ በዚያ ደረጃ…” እያለ ፍፁም የማይገባ አንድ ዓረፍተ ነገር ጀምሮ ሳይጨርስ፣ ልክ እንደሰከረ ጀብራሬ ወድያና ወዲህ ሲረግጥ ሳየው ሱዳን ውስጥ ሆኖ የተናገረውን አዲስ አበባ ላይ መድገም አቅቶት፣ ጌቶቹ ያስጠኑትን መናገር ከብዶት ሲንተባተብ ማየት ያሳፍራል፡፡ ጌቶቹን ለማስደሰት ብሎ “ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋን ያስመጣሁት እኔ ነኝ” ብሎ ፋውል ሰርቶ እርፍ አለ፡፡

ከዛም እግሩን ማከክ ጀመረ፤ እኔም ትዝብቴን ቀጠልኩኝ፡፡ ለነገሩ እንዲህ ያለ ደካማ በትግል ጓዶቹ የግምገማ መዓት ሲወርድበት፣ ስልጣን ያለ ደረጃው መያዙን ሲያውቁበት እስከዛሬ በማን አለብኝነት ሲሰራው የነበረው ስህተት መታወቂያው ሰዓት ሲደርስ እና የስልጣን እርክክብ ሲያደርግ እስከ ዛሬ ድረስ ስልጣኑን ተገን አድርጎ የሰራው ጉዱ ቢወጣ ሊያስከትልበት የሚችለውን ችግር አውቆት ማምለጥን መረጠ፤ ለጫማው በኋላ ይታሰብበታል በማለት እግሬ አውጭኝ ብሎ (በኔ ግምት ቢበዛ ከአንድ ወር ያልበለጠ ግዜ ከወያኔዎች ጋር ግንኙነት በመፍጠር) ፈርጥጦ ሲያበቃ “አንድ ዓመት ሙሉ ከወያኔ ደህንነት ጋር አብሬ እሰራ ነበር” ብሎ እንዲወሸክት እና በአንፃሩ የነሱን ጥንካሬ የሚያሳይላቸው መስሎዋቸው እንዲናገር አደረጉ፡፡ እንዲሁም አንድ ዓመት ሙሉ የሰራው ለመፈርጠጥ እንዲመቸው ሩጫ ሲለማመድ የቆየ እስከሚመስል ድረስ መላ ቅጡ ሲጠፋበት፣ እጅግ የደከመ እና ለአቅመ ፖለቲካ ፕሮፓጋንዳ ያልደረሰ ሆኖ አግኝቼዋለሁ። ይልቅስ የወያኔ የሀገር ደህንነት ነኝ ባይ ምን ያህል የደካሞች እና የኋላቀሮች ስብስብ መሆኑን ፍንትው አድርጎ የሚያሳይ ስራ ነው በራሳቸው ላይ የሰሩት፡፡ ደካማ በሆነና ውሃ በማይቋጥር ነጭ ውሸት ፕሮፓጋንዳ ሰዉን እናሞኛለን ብለው በተቃራኒው የገዛ ስራቸው እራሳቸውን ይለበልባቸው ጀመር፡፡ በአፍቃሬ ወያኔነታቸው የምናውቃቸው እነ ሪፖርተር ጋዜጣ እንኳን ሳይቀር ሠውዬው የሚናገረው የሃገር ደህንነቱንም ጥንካሬ ግምት ውስጥ የሚከት ሆኖ፧ በዚያ ላይ ለአንድ ዓመት አብረን ሰራን የሚለው እና ተገኘ የተባለው ውጤት በፍጹም ግራ የሚያጋባ ሲሆን ሠውየውን ለማስኮብለል ብቻ ይህን ያህል ግዜ ፈጀብን ከተባለ ያስገምተናል ኸረ አታዋርዱን በማለት የወዳጅ ምክሩን በሾርኒ ለገሳቸው። ከዚያም የሳምንታት እድሜ ለኢቲቪ ወሬ ማናፈሻ እንኳን ሳይሆናቸው ድምጻቸውን አጥፍተው ተቀመጡ።

ለነገሩ ድከሚ ያላት ጥቁር ሴት እጇን ትነቀሳለች እንዲሉ፣ ሰውዬውም የነሱ ቢጤ ደንቆሮ መሆኑን ሲያውቁ ኳስ በመሬት ብለው እብስ አሉ፡፡ ጨው ለራስህ ብለህ ጣፍጥ፤ አለበለዚያ እንደ ሞላ አስገዶም ይወረውሩሃል እያልኩ ሀሳቤነ በዚሁ ልቋጨው፡፡

The post ሞላ አስገዶም – ድከሚ ያላት ጥቁር ሴት እጇን ትነቀሳለች appeared first on Zehabesha Amharic.

ምኒልክ ወስናቸው እና ኾጀሊ ዑሥማን – (አፈንዲ ሙተቂ)

$
0
0

ምኒልክ ወስናቸው እና ኾጀሊ ዑሥማን – (አፈንዲ ሙተቂ)
ዛሬም በሱዳን ሙዚቃ መዝናናታችንን ልንቀጥል ነው፡፡ በዛሬዋ ምሽትም ከምድረ ሱዳን ያገኘነውን إنت صافيتنا لو مالو የተሰኘውን የምንጊዜም ተወዳጅ ዜማ እንጋብዛችኋለን፡፡ ዜማውን በቅድሚያ የተጫወተው ዝነኛው ሱዳናዊ ድምጻዊ “ኾጀሊ ዑሥማን” ቢሆንም ከታች ሊንኩን ባስቀመጥኩት የዩ-ቲዩብ ቪዲዮ ውስጥ የኛው ምኒልክ ወስናቸው አብሮት ሲዘፍን ትመለከታላችሁ፡፡ ይህንን ምርጥ ዜማ የጻፈው ሱዳኖች እንደ ብሄራዊ ገጣሚያቸው የሚያዩት ኡስታዝ ያሲር በሺር አባስ ነው፤ ዜማውን የደረሰው ደግሞ እራሱ ኾጀሊ ዑሥማን ነው፡፡ ኾጀሊ ከዚህ ዘፈን ሌላ በኢትዮጵያ፣ በኤርትራና በሶማሊያ እጅግ ተወዳጅ ሆነው በዘለቁት “ሐብባ ሐብባ” እና “ማብኒኽተሌፍ” የተሰኙ ዜማዎቹም ይታወሳል፡፡

ምኒልክ ወስናቸው በበኩሉ የሱዳን ዜማን ከሙሉ ቃላቱና ከሜሎዲው ጋር ቁጭ ማድረግ ከሚችሉት ጥቂት ዘፋኞቻችን መካከል አንዱ ነው፡፡ እኔ ፀሐፊው ከምኒልክ ሌላ የሱዳን ዘፈኖችን በትክክል ሲጫወቱ ያየኋቸው/የሰማኋቸው የሀገራችን አርቲስቶች ዓሊ ቢራ፣ ፊሊፕ ማርቲን፣ ዓለማየሁ እሸቴ፣ ኑሕ ጎበና እና ሙሐመድ ጠዊል ብቻ ናቸው፡፡ በድሮው ዘመን ዐረብኛ በሀገራችን በርካታ ከተሞች የግብይት ቋንቋ ሆኖ ያገለግል ስለነበር በርካታ አንጋፋ አርቲስቶቻችንም ቋንቋውን ለምደውታል፡፡ ይህም የሱዳን ዘፈኖችን በትክክል እንዲጫወቱ የረዳቸው ይመስለኛል፡፡ ምኒልክ ወስናቸው ግን ቋንቋውን ከመናገር በተጨማሪ በሀገረ ሱዳን የራሱን የምሽት ክበብ ከፍቶ ለአስር ዓመታት ያህል ሰርቷል፤ በመሆኑም ሱዳኖች እንደራሳቸው ሰው ነው የሚያዩት፡፡ እርሱ የሱዳኖቹን “ጃሩ አነ ጃሩ”ን በአማርኛ “ትዝታ አያረጅም” እያለ እንደተጫወተው ሁሉ ሱዳኖችም የርሱን “አደረች አራዳ” ወደ ዐረብኛ ቀይረው ተጫውተውታል፡፡ ከሁሉ አስቀድሞ “አደረች አራዳ”ን በሱዳንኛ የተጫወተው ደግሞ ሌላ ሰው አይምሰላችሁ! በዚህ ቪዲዮ ውስጥ ከምኒልክ ጋር ተጣምሮ የምናየው ኾጀሊ ዑሥማን ራሱ ነው፡፡
—-
ታዲያ ሁልጊዜ የሚገርመኝ ነገር ኾጀሊ ዑሥማን በዚህ ቪዲዮ ላይ የምትመለከቱትን ዘፈን እንደኛ እንደ ሀረር ሰዎች “እኛ” እያለ የተጫወተው መሆኑ ነው፡፡ ዘፈኑ የተዘፈነው ለአንድ ሰው ነው፡፡ ዘፋኙ “ኢንተ” የሚለው አንዲት የወደዳትን ወጣት ነው፡፡ ይሁንና ኾጀሊ ልጅቷን ያናገረው “አነ” (እኔ) በማለት ሳይሆን “ኒህና” (“እኛ”) እያለ ነው፡፡ እንዲህ ዓይነት ዘይቤ በዘመናዊው ዐረብኛ ውስጥ አይታወቅም (በጥንቱ ዘመን ንጉሦች፣ አሚሮችና ኸሊፎች “እኛ” እያሉ የሚናገሩ ቢሆንም ቃሉ ይህኛው ሳይሆን “ኢንና” የሚለው ግላዊ ተውላጠ ስም ነው፤ ይህኛው በትርጓሜው “እኛ” ማለት ቢሆንም በዚህ ቃል የሚገለጸው አንድ ግለሰብ ብቻ ነው፤ “ኒህና” ግን ምንጊዜም ብዙ ቁጥርን ነው የሚገልጸው)፡፡ እና ታዲያ ኾጀሊ “አነ” ማለቱን ትቶ “ኒህና” ያለበት ምክንያት ምንድነው?… ምናልባት ገጣሚው እንደኛው የሀረር ሰው ይሆን እንዴ? ወይስ ዘፋኙ “ኢንተ” የሚለው ወጣቷን ሳይሆን ሌላ ነገርን ነው…? እርግጡ አልታወቀም፡፡
—-
ኾጀሊ ዑሥማን እና ምኒልክ ወስናቸው አሁን በህይወት የሉም:: ስራቸው ግን ዛሬም ከኛ ጋር ነው፡፡ የሚከተለውን ሊንክ ከፍታችሁ ሁለቱ አንጋፋ ድምጻዊያን “ማሉ ሰው ሰፌትና ኢንታ”ን በጋራ የተጫወቱበትን ቪዲዮ መመልከት ትችላላችሁ፡፡

—-
ገና ሊንኩን ከመክፈታችሁ ዘፈኑን በዜማው ብቻ እንደምትለዩት ይታወቀኛል፡፡ የዘፈኑ ግጥም ካስፈለጋችሁ ደግሞ በግዕዝ ፊደላት እንደሚከተለው ተጽፏል፡፡
—–
ማሉ ለው ሰፌትና ኢንታ
ወመረህ መረህ ቢቅተ ቲጂና
ኒሕና ማቀሰርና ሐሸ
ኢንተ ኢትለወምተ ፊና (2)
ኢንተ ኢትለወምተ ፊና

ወበዕደከል አያም ሐዚነህ-2
ሸይለ ኩልለ ዱነያ አሃ-2
ላ ሰባሕ ጠላሃ በዕደክ
ያ ሐናነ አል-ሬድ ገሽሻሃ
(solo Music)
ማሉ ለው ገልበክ ቲራና-
ቲስወተል አያም ኒሳሃ
ኒሕና ፊ ሬደክ ሺጊና
ኢንተ ኢትለወምተ ፊና
ኢንተ ኢትለወምተ ፊና
***
አድ-ደርቢ ሚራት የጂበክ-(2)
ወኢንተ ማቃሲድ ተጂና-(2)
መርረ ሹፍነክ ወኢንተ ማሪ
ዚ ነዳዋት ኻጥረህ ፊና
(solo music)
ኒሕና ፊ ደምዓት ጊሪቅና
ወኢንተ ዚመሐትረ ፊና
አላህ ዪህዲክ ያ መዐሌና
ኢንተ ዪልቀሰርነ ፊና
ኢንተ ኢትለወምተ ፊና
—–
ጭሮ- ምዕራብ ሀረርጌ
ጥቅምት 7/2008

The post ምኒልክ ወስናቸው እና ኾጀሊ ዑሥማን – (አፈንዲ ሙተቂ) appeared first on Zehabesha Amharic.

ድፍን የአዲስ አበባን ህዝብን ያስለቀሰ የመኪና አደጋ –ልትወልድ ቀናት የቀሯት ወጣት ሕይወቷ ተቀጠፈ

$
0
0

 

yewebdar
በኢትዮጵያ እየወጡ መቅረት የተለመደ ሆኗል – በተለይ በመኪና አደጋ:: ከ ዕለት ወደ እለት በሃገሪቱ በሚደርሰው የመኪና አደጋዎች በርካቶች ሕይወታቸው እያለፈ ነው::

ከላይ በፎቶ ግራፍ የምትመለከቷቸው ሁለት ጥንዶች ዳንኤልና የወብዳር ይባላሉ።ከ8 ወር በፊት እጅግ ደማቅ በሆነ ሁኔታ የሰርግ ስነስርአታቸውን አክብረዋል።
ዮብዳር በአንድ የመንግስት መስሪያ ቤት ሰራተኛ ነች ። በማኔጅመንት የመጀመሪያ ዲግሪዋን በማታው የትምህርት ዘርፍ በመከታተል ላይ ነበረች ።
ወጣቷ ልጅ ወልዶ የመሳም ጽኑ ምኛት ነበራት ይህንንም ለማሳካት ጥቂት ቀናት ነበር የቀራት ሆንም ግን በትናንትናው እለት ቀትር ላይ ኦሎምፒያ ሸዋ ዳቦ አካባቢ በደረሰባት አሳቃቂ የመኪና አደጋ ህይወቷ አልፏል ።
የቀብር ስነስርአቷም በዛሬው እለት በቀጨኔ መድሀኒያለም ቤተክስቲያን 9 ሰአት ላይ ይፈጸማል።

በኢትዮጵያ እየደረሰ ያለው የመኪና አደጋ እጅግ አሰቃቂ ነው:: ሰው አምኖ ለመንዳትም ሆነ ለመሳፈር እየተቸገረ ያለበት ሁኔታ ብቻ ሳይሆን በመንገድ ላይ መሄድ የሚያስፈራበት ደረጃ ላይ ተደረሷል:: በቀጣይ የምትመለከቱት ፎቶ ግራፍ በቅርቡ አገልግሎት መስጠት የመጀመረው ባቡር መንገድ ላይ የገባውን አውቶቡስ ነው::

babur

The post ድፍን የአዲስ አበባን ህዝብን ያስለቀሰ የመኪና አደጋ – ልትወልድ ቀናት የቀሯት ወጣት ሕይወቷ ተቀጠፈ appeared first on Zehabesha Amharic.

ኤርትራዊው ወጣት እስራኤል ውስጥ “በሰህተት እና በግፍ “መገደሉ ታላቅ ቁጣ አስነሳ

$
0
0

ከታምሩ ገዳ

“ይህ አይነቱ አረመኔያዊ ግድያ ድብቅ እንጂ አዲስ ነገር አይደለም ።” የ ኤርትራ ማስታወቂያ ሚ/ር

ከዛሬ አራት አመት በፊት ከትውልድ አገሩ ኤርትራ ባሕር እና የብስ አቋርጦ ወደ “ተሰፋይቱ ምድር” እስራኤል ለተሻለ ኑሮ ሲል የተሰደደው የ29 አመቱ ሃብቶም ዘረሁን በቀጣሪዎቹ ዘንድ “ተግባቢ ፣ ለመሻሻል የሚጥር እና በጣም ተወዳጅ ወጣት ነበር ።” እንደ አሱሶትድ ፕሬስ ዘገባ ሃብቶም የሰራ ቪዛውን ካሳደሰ በሁዋላ እስራኤል ውስጥ ያጠራቀማው ገንዘቡን ይዞ በኤርትራ የሚገኙ ቤተሰቦቹን በቅርቡ ለመጠየቅ እቅድ ነበርው ።
Eri
ይሁንና ሰው ያስባል አግዚአብሔር ይፈጽማል እንዲሉ ባለፈው እሁድ ጥቅምት 18 2015 እኤእ አመሻሹ ላይ እስራኤል (ቤርሳባ ውስጥ) አንደ ፈለሰጤማዊ እስራኤል በአንድ አውቶቡስ ማቆሚያ አካባቢ አንድ የእስራኤል ወታደር መሳሪያውን ነጥቆ እና ተኩሶ ገደሎ ፣ 10 አቁሰሎ እራሱ (ገዳዩም) በጸጥታ ሃይሎች የተገደለበት ገጠምኝን /ግጭትን በአቅራቢያ የታዘበው ወጣቱ ሃብቶም ከግርግሩ ለማምለጥ ሲጣጣር የተመለከተው አንድ የእስራኤል የጥበቃ ሰራተኛ ሃብቶምን “ከአሸባሪዎች አንዱ ይሆናል “በማለት በጥይት ተኩሶ የዘርረዋል።ከደረሰበት ጉዳት ሳቢያ ሰውነቱ በደም የታጠበው ሃብቶም አስቸኳይ የህክምና እርዳታ ሊሰጠው ሲገባ (በትንሹ አንድ ፖሊስን ጨምሮ) በሰፍራው የነበሩ የተወሰኑ ሰዎች የጥላቻ ቃላት በመጠቀም ፣ በመተፋት እና ከአካባቢው የነበሩ ቁሳቁስ(ወንበር ሳይቀር) በማነስት የደበድቡታል። በጸታ ሃይሎች እና በሰላም ወዳዶች ጣልቃገብነት ከሰፈራው የተወሰድው ምስኪኑ ሃብቶም ሃኪም ቤት እንደደረሰም ብዙ ሳይቆይ እሰከ ወዲያኛው አሸልቧል።

ያ እሩቅ እላሚው እና የ 29 አመቱ ሃብቶም በድንገት መሞት የአስራኢል፣የኤርትራ እና የፍልስጤም ፖልቲከኞችን አናቁሯል ። የሰብእዊ መብት ተሟጋቾችንም በእጅጉ ኣሳዝኗል። የእስራኤል ጠ/ሚ/ር ቢኒያም ናቲናያሁ በደረሰው ደንገተኛ አደጋ የተሰማቸውን ሃዘን ለሟች ቤተሰቦች በላኩት መልክት የገለጹ ሲሆን “አገራችን እስራኤል በሕግ የበላይነት ታምናለች።” ያሉት ጠ/ሚ/ሩ ድርጊቱንም የፈጸሙ ወገኖች በአስቸኳይ ለፍርድ እንደሚቀርቡ ቃል ገብተዋል። የወንጀለኞቹ ማንንነትን ለማጣራት የቪዲዮ ምስል ምርመራ በመካሄድ ላይ ሲሆን እስከ እሁን ድረስ ግን አንድም ተጠረጣሪ አልተያዘም ተብሏል።

የፈልስጤም ራስ ገዝ ከፍተኛ ባለሰልጣን የሆኑት ሃና አሽራዊ “የእስራኤል ባለሰልጣናት ሕዝቡን ጥላቻ እና ወንጀል እየመገቡት ለእንደዚህ አይነቱ ድርጊት ደረሰዋል” በማለት ሃላፊነቱ የባለሰልጣናቱ መሆኑን ተናግረዋል።የኤርትራ ማሰታወቂያ ሚ/ር በበኩሉ ሰኞ ጥቅምት 19 /2015 አኤአ ባወጣው መግለጫው “ ይሂ ጭካኔ እና ዘግናኝነት የተሞላበት የግደያ ድርጊት በእስራኤል በሚገኙ 10ሺዎች ሰላማዊ ዜጎች ላይ ከህዝብ እይታ ውጪ እለት ተእለት የሚፈጸምባቸው እርምጃ አንዱ አካል ነው።ኤርትራዊያን ዜጎች ካለፉት ጥቂት አመታት ወዲህ በሕገ ወጥ አዘዋዋሪዎች እየተወናበዱ ለፖሊቲካ ፍጆታ እና ለእስራኤል ርካሽ የጉልበት ሰራተኛነት ተዳርገዋል።” በማለት የተላቪቭ መንግስትን ኮንኗል።

የመብት ተሟጋቹ ሁማን ራይት ዎች አንዲሁ “ ሃብቶም ጥገኝነት ፈለጋ ወደ እስራኢል ተሰዶ በእስራኢል ደህነቶች እና በጋጠወጦች መገደሉ ተቀባይነት የለውም ።” ሲል ተቃውሞውን አሰምቷል ። አሚንስቲ ኢንተርናሽናልም “ሃብቶም የሞተው ቆዳው በመጥቆሩ ብቻ ነው፣ገዳዮቹም ባስቸኳይ ለፍርድ ይቅረቡ ።” ብሏል ።በዛሬይቱ እስራኤል ወስጥ ከ 34ሺህ በላይ ኤርትራዊያን እንደሚኖሩ ዘገባዎች ይገልጻሉ ። በሰሞኑ የእስራኤሎች እና የፈልስጤሞች ግጭት ከ 44 በላይ ፈልስጤሞች ሲገደሉ ከ 9 በላይ እስራኤሎችም ሕይወታቸውን አጥተዋል። ሁኔታው ያሰጋቸው የተመድ ዋና ጸሃፊ ባን ኪ ሙንም ውጥረቱን ለመዳኘት ወደ ሰፍራው ለማቅናት ተዘጋጅተዋል።

የተቃዋሚው አኦፈር ሻለህ ሊቀመንበር የሆኑት ያሽ አቲድ”ተጠርጣሪ ግልሰብ በጸጥታ ሃይል ተመቶ ከቆሰለ በሁዋላ አደገኛነቱ አናስተኛ መሆኑ እየታወቀ አንድን ግለሰብ(ሃብቶምን) ከወደቀበት እያቃሳተ ሳለ ለሞት እስኪያበቃው ድረስ በቡድን መደብደብ ፍጹም ተቀባይነት የለውም ፣ይህንንም ህግ ማንኛውም የእስራኤል ወታደር ጠንቅቆ ያውቀዋል።”ብለዋል።

መርቲዝ የተባለው ፓርቲ ዋና ጸሃፊት የሆኑት ዚሃቫ ጋለን “የመከላከያ ሚ/ሩ በቅርቡ ሲቪሎች ሁሉ የጦር መሳሪያ ይታጠቁ ማለታቸውእና የትምህርት ሚ/ሩ ደግሞ (እንደ ካው ቦይ) ሸጉጥ ታጥቀው ፎቶ መነሳታቸው ምን ያህል ከእውነታው እርቀን በ እብደት አለም ውስጥ እንዳለን ያመላክታል።”በማለት የወቅቱ ፖለቲከኞችን በጽኑ ኮንነዋል።የጺዮናዊነት ሕብርት የተሰኘው ቡድን የሚወክሉት ማክ ናችማን ሻይ በበኩላቸው “ይህ እረዳት የሌለው ፍጡር (ሃብቶም) ከመሬት ላይ ተንጋሎ ሳለ ደብደቦ መግደል ሰበዊነት አይደለም ፣የ አይሁዳዊያን ባሕሪም አይደለም ።” በማለት የአገሪቱ ዋናው አቃቢ ህጉ በግድያው ዙርያ ልዩ ማጣራት አንዲያካሁዱ በደብዳቤ ጠይቀዋል።እለታዊው የእስራኤል ጋዜጣ ዮዲት “ሃብቶም የተገደለው ያለ አንዳች ጥርጥር በቆዳው ቀለም ልዩነት ሳቢያ ነው። “ሲል አስነብቧል።

ደርጊቱን ፈጽመዋል ተብለው ከተጠረጠሩት መካከል አንዱ እንደሆነ አና “ዱዱ”በሚል ሰም አንዲጠራ የጠየቅው ግለሰብ ለእስራኤል ጦር ሃይል ራዲዮ በሰጠው እማኘነት “ግለሰቡ(ሃብቶም) አሸባሪ አለመሆኑን ባውቅ ኖሮ ጫፉን አልነካውም ነበር። አሁን ግን በእጃችን ህይወቱ ያለፈው ግለሰብ(ሃብቶም) ነጹህ ሰው መሆኑን ከተረዳሁ በሁዋላ እንቅልፍ መተኛት ተሰኖኛል” በማለት መጸጸቱን ተናግሯል።

ሃብቶምን ከወርበሎች ለመታደግ ጥረት አድርጎ እንደነበር የሚናገርው መርሰኮ የተባለ መንገደኛ በበኩሉ ለቻናል 10 ቴሊቪዥን በሰጠው አስተያየት “ቁም ነገሩ ግለሰቡ (ሃብቶም) አሸባሪ ይሁን አይሁን አይደለም ግለሰቡ መንቀሳቀስ አቅቶት ተኝቶ እየተዪ በሰሜታዊነት ተደብድቦ መሞቱን በአይኔ በመመልከቴ ውስጤ ተጎድቷል ፣እንቅልፍም እርቆኛል።” በማለት በሁኔታው የሰነልቦና መታወክ እንደገጠምው ገልጿል።

የሟች ሃብቶም አለቃ የሆኑት ሳጂ ማላቺ እንዲሁ በበኩላቸው ሃብቶም ወደ ደቡባዊ እስራኤል (ቤርሳባህ )የተጓዘው የሰራ ፈቃዱን ለማስደስ አንደ ነብር አወስተው “ ”ጭምት እና ሃላፊነቱን ዘወትር ለመወጣት የሚጥር ታታሪ ሰራተኛ ነበር። ሃብቶም በማያወቀው ሰፍራ እና ባለጠበቀው ሰአት ሀይወቱ እንደቀላል ነገር በማለፉ ልቤን ክፉኛ ነክቶታል ።”ሩቅ አልሞ በ ጽጥታ ሃሎች ተተኩሶበት እና በወርበላዎች ተደብደቦ በአጭሩ ለቀረው ሰራተኛቸው እና ወዳጃቸው ለነበረው ሃብቶም ያላቸውን ፍቅር እና ሃዘናቸውን ገልጸዋል።
ፈጣሪ ነፍሱን ይማረው !!!!።

The post ኤርትራዊው ወጣት እስራኤል ውስጥ “በሰህተት እና በግፍ “መገደሉ ታላቅ ቁጣ አስነሳ appeared first on Zehabesha Amharic.

Viewing all 15006 articles
Browse latest View live