Quantcast
Channel: Ethiopian News | ዘ-ሐበሻ | Latest News Provider | News For All
Viewing all 15006 articles
Browse latest View live

(ሰበር ዜና) የኢትዮጵያ ወታደራዊ አውሮፕላን ተከሰከሰ

$
0
0

Plane crash

(ዘ-ሐበሻ) በሶማሊያ ዋና ከተማ ሞቃድሾ በማረፍ ላይ የነበረ አንድ የኢትዮጵያ ወታደራዊ አውሮፕላን ዛሬ ማለዳ ላይ  መከስከሱን ከአዲስ አበባ የመጡ ዜናዎች አረጋገጡ። የኢትዮጵያ መንግስትም ይህንን ዜና ያረጋገጠ ሲሆን የሟቾች ቁጥር 4 መድረሱንም አስታወቋል።

የወታደራዊ እቃ ማጓጓዣ አውሮፕላኑ አደጋ የደረሰበትለማረፍ በሚሞክርበት ወቅት እንደሆነ ዓለማቀፉ የሚዲያ ተቋም ሮይተርስ ሲዘግብ በአውሮፕላኑ ውስጥ ተጭነው ከበነበሩ 5 ሰዎች ውስጥ 4ቱ ሕወታቸው ማለፉም ተዘግቧል።

(ተጨማሪ መረጃ እንደደረሰን እንመለሳለን)

↧

↧

ስንቅና ውሸታም እያደር ይቀላል! –ፈቃዱ ለሜሣ (ፕሮፌሰር)

$
0
0

የኮርስ ስም ፤ በኢትዮጵያ የኦሮሞ ማኅበረሰብ ላይ የሚሠነዘሩ የፈጠራ ወሬዎችና ተጨባጩ ሃቅ
የኮርስ ቁጥጥር ፤ ‹hist101› (ልቦለድና ፈጠራ በኢትዮጵያ ኦሮሞዎች ላይ)
የኮርስ መምህር፤ ፕሮፌሰር ፈቃዱ ለሜሣ
ኮርሱ የተጀመረበት ወር፤ ሐምሌ 2005
ትርጉምና ቅንብር፤ ይነጋል በላቸው

ማሳሰቢያ፡- አሁን እዚህ ያቀረብኩት የትርጉም ሥራ ከወቅቱ የፖለቲካ ንፋስ አኳያ በጣም ጥንቃቄ የሚያስፈልገው መሆኑን አውቃለሁ፡፡ በቃላት የምንዛሬ ትርጉም ዜጎች እየተላለቁ በሚገኙባት ሆደባሻ ዓለም ውስጥ ይህን መሰሉን ጉዳይ በቀላሉ መተርጎም እንደማይቻል እረዳለሁና ማንኛውም ዓይነት በዋናው ጽሑፍ ላይ ያልተጠቀሰ ሃሳብ በዚህ ትርጉም ውስጥ በስህተት ቢገኝ ኃላፊነቱ ፕሮፌሰሩ ሣይሆን የኔ የተርጓሚው መሆኑን ለአንባቢያንና ለፕሮፌሰር ፈቃዱ ከታላቅ ይቅርታ ጋር በትህትና እገልጻለሁ፡፡ በተቻለኝ መጠን የዋናው የእንግሊዝኛ ጽሑፍ ወዘና እንዳይጠፋ ጥረት አድርጌያለሁ – የኔ የራሴ ሥነ ልሣናዊ ‹የተፈጥሮ ለዛ›ም እንዳይከፋብኝ ከሚል ቅን አስተሳሰብ በመነሣት የተጠጋጋ ግን ከዋናው እምብዝም የማያፈነግጥ ‹ኮዝሞቲክስ› እጅግ አልፎ አልፎ በጣም በስሱ ፈንጠቅ ለማድረግ ሞክሬያለሁ – ለዚህ ደግሞ ፕሮፌሰርን በድጋሚ ይቅርታ እጠይቃለሁ – እንዲህ የማደርገው እንግሊዝኛው ወዳማርኛ ሲመለስ ድርቅ እንዳይልብኝና መሸጋገሪያ ድልድዩ ቢጠናከር ትርጉሙ ይበልጥ እንደሚያምር ሳምንበት ነው ፤ ለማንኛውም ግን ሰው ነኝና ብሳሳት በቀናነት እዩልኝ እንጂ ልፋቴን በሚያጣጥል የከፋ ደረጃ እንዳታብጠለጥሉኝ አደራ እላለሁ፡፡ ዛሬም መልካም ንባብ፡፡

OLF rebels from the front-line hold their weapons as they return to their training camp in Southern Ethiopia near the border town of Moyale(ኦሮሞዎችንና የኢትዮጵያን ታሪክ በሚመለከት ዳሰሳ ለሚያደርጉ የውጭ ጋዜጠኞች የመነሻ ግንዛቤ መጨበጫ ይሆናቸው ዘንድ የተዘጋጀ) ኦሮሞና ኢትዮጵያ፤ ምሥጋና ለ: ayyaantuu.com ድረ ገጽ)

(ናዝሬት፣ ኢትዮጵያ) – መሠረቱን ኳታር ያደረገው የአልጀዚራ ቴሌቪዥን የኢትዮጵያ ኦሮሞዎችን በሚመለከት በርካታ ዝግጅቶችን በቅርቡ አየር ላይ ማዋሉ የሚታወስ ነው፡፡ የሕዝባችንን ገጽታ በመሰለው መልክ ለዓለም ማኅበረሰብ በስፋት በማስተዋወቅ ረገድ ይህ የሚዲያ ተቋም የመጀመሪያው በመሆኑና እያደረገ ያለውም አስተዋጽዖ ቀላል ባለመሆኑ ሊወደስ ይገባዋል፡፡
ይህ ዓይነቱ ሕዝብን የማስተዋወቅ ሥራ ከሚያስገኛቸው ጠቀሜታዎች ውስጥ አንደኛው፣ የሀገሪቱ ባለሥልጣናት በነሱና በተከታዮቻቸው አማካይነት በሕዝቡ ላይ እየደረሰ የሚገኘውን ግፍና በደል እንዲሁም የሰብኣዊ መብት ጥሰቶች የሚከታተል ገለልተኛ ወገን መኖሩን ተገንዝበው የሚያካሂዷቸውን የሰብኣዊ መብት ረገጣዎች በቀላሉ እንዳይመለከቱ ማስገደዱና በዚያም ሳቢያ እነኚሁ ባለሥልጣናት የሚያስተዳድሩትን ሕዝብ የወቅት ሁኔታ የዓለም ሕዝብ በግልጽ እየተከታተለው መሆኑን እንዲያውቁት ማስቻሉ ነው፡፡ ኦሮሞዎችና ሌሎች ኢትዮጵያውያን በጋራ ሆነው ለእኩልነትና ለዴሞክራሲያዊ መብቶቻቸው መከበር ላለፉት በርካታ አሠርት ዓመታትና አሁንም ድረስ ሲታገሉ ቆይተዋል፡፡ ስለኦሮሞ ሕዝብ ጥንተ አመጣጥና ታሪካዊ ዳራ የመዘገቡ አስፈላጊነት ጥያቄ ውስጥ የማይገባ መሆኑ እንዳለ ሆኖ ይህ ሲደረግ ግን በትክክል መዘገብ እንደሚኖርበት መረዳት ለማንኛውም ወገን ጠቀሜታ አለው፡፡ ትክክለኛ ያልሆነና የተጣመመ መረጃን ወይም በማወቅም ይሁን ባለማወቅ ወደ አንድ ወገን የሚያጋድል ዘገባን ማቅረቡ ለዴሞክራሲ የምናደርገውን ሁለንተናዊ ትግል ይጎዳብናልና ከዚህ መሠረታዊ ነጥብ አንጻር ሁላችንም ከፍተኛ ጥንቃቄ ማድረግ ይገባናል፡፡ ይህ የተንሻፈፈ አካሄድ ብሔራዊ መግባባትንና ሰላምን ከመፍጠር ይልቅ ቁጣንና አንዱ ባንዱ ላይ መንገፍገፍን እያስከተለ ቅራኔን ያባብሳል፡፡
በቅርቡ አልጀዚራ ትክክል ያልሆነ ወይም የተሳሳተ ዘገባ እንዲያርቀብ ከተገደደበት ምክንያቶች አንደኛው የመረጃ ምንጩ ግራና ቀኙን ያማከለ ሣይሆን በአንድ አቅጣጫ ብቻ ማለትም በአብዛኛው በዉጭ የሚንቀሳቀሱ ኦነግንና ኦ.ኤፍ.ዲ.ኤምን የመሳሰሉ የኦሮሞ ድርጅቶች መሆናቸው ነው፡፡ በዚህ ግን አልጀዚራ ብዙም ሊወቀስ አይገባውም፤ ምክንያቱም በኢትዮጵያ የሚገኙ ትክክለኛውን መረጃ የሚያውቁ ሰዎች ወይም ድርጅቶች የሚያውቁትን እውነት ቢናገሩ የሚደርስባቸውን ያውቃሉና ለደኅንነታቸው ይሰጋሉ፡፡ ስለዚህም አልጀዚራን የመሳሰሉ የውጪ የመገናኛ ብዙኃን የተሻለ አማራጭ ሲያጡ በመረጃ ምንጭነት ለመጠቀም የሚገደዱት በውጭ ሀገራት በስደትና በልዩ ልዩ ኢኮኖሚያዊም ይሁን ፖለቲካዊ እንቅስቃሴዎች ላይ ተሠማርተው የሚገኙ ሰዎችን ወይም ቡድኖችን ነው፡፡ ይህ ደግሞ ኢትዮጵያን የመሳሰሉ የሦስተኛው ዓለም ሀገራትን ሁኔታ መዘገብ ለሚፈልጉ ለእንደነዚህ ዓይነቶቹ የውጭ የመረጃ ተቋማት ትልቁ የራስ ምታት ነው፡፡ ምክንያቱም ከአንድ ወገን የሚያገኙትን መረጃ ሊያረጋግጡ የሚችሉባቸው የሀገር ውስጥ በሮችና መስኮቶች በሚዲያ አፋኝ አምባገነን መንግሥታት ስለሚዘጉባቸው በአብዛኛው ያልተረጋገጠና የአንድ ወገን መረጃ ለመዘገብ ይገደዳሉና፡፡
ለዛሬው ለመማማር ያህል እንዲጠቅመን ሰሞኑን አልጀዚራ በኦሮሞ ሕዝብ ታሪክና ለዴምከራሲያዊ መብቶቻችን መከበር በምናደርገው ትግል ዙሪያ ያስተላለፋቸውን ዘገባዎች በሚመለከት መታረም የሚገባቸው ዋና ዋና ህፀፆችና እውነትነት ጨርሶውን የሚጎድላቸው አሳሳች ጉዳዮች ስላሉ በነዚያ ላይ አንዳንድ የማስተካከያ ነጥቦችን ከዚህ በታች እንመለከታለን፡፡ የሚከተሉት የማስተካከያ ሃሳቦች ከፖለቲካዊ አስተሳሰብ በጸዱ ሃቀኛ ምሁራን የሚደገፉ ቢሆኑም በፖለቲካ ጠበል የተጠመቁ የማንኛውም ጎራ ‹ምሁራን› ግን ላይደገፏቸው ወይም ተቀባይነት ሊያሳጧቸው ይችላሉ፡፡ ይሁንና እነዚህን ሃቆች ማንም ይገፍትራቸው ወይም ይቀበላቸው ዋናው ጉዳይ እውነታዎቹ ስሜት ወለድ ሳይሆኑ የታሪክ መዛግብትን፣ የአውሮፓ ተመራማሪዎች የደከሙባቸው የታሪክ መጻሕፍትንና በዕውቅ ምሁራን የተዘገቡ የታሪክ ማስታወሻዎችን መሠረትና ዋቢ ያደረጉ በመሆናቸው የትኛውም ወገን ሊጠራጠራቸው አይገባም፡፡

ልቦለድ ቁጥር አንድ:-

“ እንደ አውሮፓውያን የዘመን አቆጣጠር ከ1868 እስከ 1900 ከጠቅላላው የኦሮሞ ሕዝብ መካከል ግማሹ የሚሆነውና ወደ አምስት ሚሊዮን አካባቢ የሚገመተው ሕዝብ ሙሉ በሙሉ [በሀበሾች ንጉሥ በአጤ ምኒልክ ጦር]ተገደለ፡፡”

ሃቅ ቁጥር አንድ፡-

ይህ መነሻና መድረሻ የሌለው ተራ አሉቧልታ እንጂ እውነት አይደለም፡፡ ይህንና ሌላም ይህን መሰል መሠረተቢስ ወሬ ተደጋግሞ የሚነገረውና እንደማለፊያ ዜማ ዘወትር የሚቀነቀነው በአብዛኛው የኦሮሞን መገንጠል በሚደግፉና ዓላማውንም በሚያራምዱ ‹ተምረናል› በሚሉ የተወሰኑ የኦሮሞ ማኅበረሰብ አባላትና ውጪ ባሉ አክራሪ የጎሣ ፖለቲካ አቀንቃኞች እንዲሁም ‹gadaa.com›ን በመሳሰሉ የኦነግ ደጋፊ ድረ ገፆች አማካይነት ነው፡፡ የሆኖ ሆኖ ግን እነዚህ ወገኖች በዚያን ዘመን የተገደለው የኦሮሞ ቁጥር አምስት ሚሊዮን ማለታቸው የቁጥር ዕውቀታቸው ዜሮ መሆኑን ከማመልከቱ ባሻገር የሚያስተላልፈው መልእክት ሚዛን የሚያነሳ እንዳልሆነ ታሪክንና የሕዝብ ብዛት ዕድገትን የሚያውቅ ይረዳዋል፡፡ በዚያን የ19ኛው መቶ ክፍለ ዘመን መገባደጃ አካባቢ 90 የሚደርሰውን የኢትዮጵያን ዘውጎች ሁሉንም ሥሌት ውስጥ ባካተተ የሕዝብ ቆጠራ ጠቅላላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ቁጥር ከአምስት ሚሊዮንም በጣሙን የሚያንስ እንደነበር በታሪክ መጻሕፍት ሠፍሮ ይገኛል፡፡ እውነቱ ይህ ሆኖ ሳለ ታዲያ ከዘጠናው ዘውግ ውስጥ የኦሮሞው ማኅበረሰብ ብቻ ተነጥሎ “10 ሚሊዮን ይደርስ ነበር፤ ከዚያም ውስጥ አምስቱ ሚሊዮኑ በ‹ጨካኝ ንጉሥ ተጨፍጭፎ› ተገደለ” ማለቱ በራሱ የጤናማነት ጉድለት እንጂ አንድም ተጠየቃዊ አመክንዮ የለውም፡፡ ለመዋሸት ደግሞ ይህን ያህል ረጂም ርቀት መሄድ ለምን እንዳስፈለገ ለማንም ግልጽ አይመስልም፡፡ ስለዚህ አምስት ሚሊዮን ኦሮሞዎች በአፄ ምኒልክ ጦር ተገደሉ የሚለው የተሳሳተ መረጃ የማንንም ቀልብ የማይስብና የትኛውንም ዓላማ ለማራመድ የማያገለግል ተራ የፈጠራ ወሬ ነው፡፡ እውነቱ ግን በዚያን ዘመን በተቀሰቀሱ የገብር አልገብርም የርስ በርስ ግጭቶችና ጦርነቶች ሳቢያ በብዙ ሺዎች የሚገመቱ ኦሮሞዎችና ሌሎች ኢትዮጵያውን – በሁለቱም ጎራዎች – ለሕልፈት መዳረጋቸው ነው፡፡ አንዳንድ ፖለቲከኞች ለራሳቸው ጠባብ አጀንዳ ሲሉ የዚያን ጊዜውን ዕልቂት ‹ጄኖሣይድ› እንደሆነ ቢፈርጁም እውነቱ ግን ሌላ ነው፡፡ እውነቱ ታዲያ የጄኖሣይድ ሣይሆን በዘመኑ በአውሮፓ መሣሪያና በሰለጠነ የሰው ኃይል ተደራጅቶ የነበረው በንጉሠ ነገሥት ምኒልክ የሚታዘዘው የሸዋ ጦር በኋላቀር መሣሪያና ካለበቂ የጦር ልምድና ሥልጠና ለጦርነት ከተሰለፈው የደቡቡ ኃይል ጋር በተፈጠረ የኃይል ሚዛን መበላለጥ ምክንያት በተከሰተው ግጭት በተለይ በደቡቡ በኩል ብዙ ወገን ማለቁ ነው፡፡ ይህ ደግሞ ባልተመጣጠኑ ኃይሎች መካከል የተከሰተን ጦርነት ወይም ግጭት ያመለክታል እንጂ አንድ የታጠቀ ዘመናዊ ጦር ለልዩ ተልእኮ ወደ አንድ መንደር ወይም ቀየ ገብቶ ባዶ እጃቸውን በቤታቸው የተቀመጡ ንጹሓን ዜጎች እንደፈጀ በማስመሰል የዚያን ጊዜውን የርስር በርስ ውጊያ ወደ‹ጄኖሳይድ›ነት ለውጦ የተለዬ ስዕል መፍጠር ተገቢ አይደለም ብቻ ሣይሆን ጥፋት ነው፡፡ ታሪካዊ እውነቱ የዚያን ዓይነት መልክና ቅርጽ የነበረው አይደለም፡፡ እንዲያውም በነዚያ ያለፉ የመከራ ዓመታት ኦሮሞ ባልሆኑ ሰዎች ከተገደሉ ኦሮሞዎች ይልቅ በኦሮሞዎች የተገደሉ ኦሮሞዎች ቁጥር በጣም ይበልጣል፡፡ ምክንያቱም በኦሮሞ የተለያዩ ነገዶች ውስጥ በሀብትም ይሁን በአስተዳደር የእኔ እበልጥ እኔ እበልጥ ፉክክርና መቀናቀን ስለነበር ከጎረቤቶቻቸው ኦሮሞዎችና ከሲዳማዎችም የነበራቸውን ሽኩቻ በጠረጴዛ ዙሪያ የቃላት ድርድር ሳይሆን አንዱ አንዱን በኃይል በመጨፍለቅ የበላይነቱን ለማረጋገጥ ሲል በጦር መሣሪያ ይፋለሙ ስለነበር ነው፡፡የዚያ ዓይነቱ ወንድም በወንድሙ ላይ ‹የሚቀዳጀው› ግንጥል ጌጣዊ ድል ደግሞ በአፍሪካ የመጀመሪያው እንዳልሆነና የተፈጥሮ ሀብትንም ይሁን ሌላ ጥቅም የሚያስገኝን ነገር ለመቀራመት ሲባል በሚደረግ ፍልሚያ በሌሎች የኢትዮጵያ ጎሣዎችና ነገዶች መካከልም የከረሩ ግጭቶች ይካሄዱ እንደነበር ታሪክ ይመሰክራል፤ ስለሆነም በደቡቡ ይበልጡን ኦሮምኛ ተናጋሪ በነበረው ማኅበረሰብና በሸዋው ባመዛኙ አማርኛ ይናገር በነበረው የአንዲት ሀገር ዜጎች መካከል የታዩ ግጭቶችን በሀገሪቱም ሆነ በሌላው ዓለም እንዳልታዩ ልዩ ተዓምሮች በመቁጠር ይህን ያህል ግዘፍ ነስተው መራገባቸው ማንንም ስለማይጠቅም እውነቱን ከእውነተኛ ምንጮች መረዳት አይከፋምና በተለይ በዚህ ቅንነት በሚጎድለውና የተንኮል ሤራ በተሸረበበት የጥፋት ጎዳና የሚራመዱ ወገኖች በአፋጣኝ ወደቀናው መንገድ በጊዜ እንዲመለሱ ይመከራሉ፡፡ ይህን ሃሳብ ጠቅለል ለማድረግ፣ የጂማ ዩኒቨርስቲው ፕሮፌሰር ጳውሎስ መንግሥቱ የቀኝ ክንፍ የኦሮሞ ነጻነት ጎራን ፍልስፍና በሚመለከት ውብ በሆነ አገላለጽ በጽሑፍ ካስቀመጡት ሀተታ ውስጥ የሚከተለውን ቀንጨብ አድርገን እንመለክት፡-

የኦሮሞን ማኅበረሰብ ታሪክ በሚመለከት ሆን ተብለው ተንሻፍፈው የተጻፉ ወይም የሚነገሩ በርካታ የፈጠራ ድርሰቶችና ልቦለዶች አሉ፡፡ እነዚህ በሬ ወለደ ዓይነት አሉታዊ ጥላ ያነገቡ የውሸት ታሪኮችን በጭፍን ተቀብለውና እውነት እንደሆኑ አምነው በጭፍን የሚጓዙ ወገኖችም ሞልተዋል፡፡ የፖለቲካ ኪሣራ ያጋጠማቸውና ወደጎን የተተው እንደኦነጉ አሰፋ ጃለታን የመሰሉ አስመሳይ ‹የታሪክ ተመራማሪዎች›ና ‹ጸሐፊዎች› በቤተ ሙከራዎቻቸው የፈበረኳቸው እነዚህ የሀሰት ወሬዎች የየዋሃንን ቀልብ በመሳብና በማሳሳት ረገድ የተጫወቱትና እየተጫወቱ ያሉት አሉታዊ ሚና ቀላል አይደለም፡፡ ይህ በስም የተጠቀሰ ግለሰብ በተለይ፣ አንድን ነገር ሆን ብሎ በማጣመም ለራሱ በሚያመቸው መልክ በመጥቀስና ቃላትን ወይም አባባሎችን ከቆሙለት ዐውዳዊ ፍቺ ሌላ ያልተፈለገ ትርጉም በማሸከም ሰውን የሚያወናብድ አሳሳች ሰው ነው፡፡ አንድ ምሳሌ ወስደን እንይ፤ አሌክሳንደር ቡላቶቪች የተባለ የ19ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ሩሲያዊ ሰው በኢትዮጵያ ውስጥ ተከሰተ ባለው በሽታና ርሀብ እንዲሁም በኦሮሞ ጎሣዎች መካከል ተካሄደ የተባለን ግጭት ጨምሮ ኦሮሞዎች ከሌሎች የሀገሪቱ ጎሣዎች በተለይም ከአማራው ጋር አካሂደዋል በሚላቸው ጦርነቶች ሳቢያ የኢትዮጵያ ሕዝብ ግማሽ በግማሽ እንዳለቀ ‹ምሁራዊ ግምቱ›ን ሰጥቶ ነበር፡፡ አጅሬ አሰፋ ጃለታ ይህን ዘገባ ካነበበ በኋላ ከአንድ ጤናማ ሰው በጭራሽ በማይጠበቅ ሁኔታ አጣምሞ በመተርጎም “ግማሹ የኦሮሞ ሕዝብ በ‹ክፉዎቹ› አማራዎች ተጨፍጭፎ ተገደለ፡፡” በማለት በኦሮሞ ታሪክ ውስጥ የግል ፈጠራ ድርሰቱን ሰንቅሯል፡፡ ይህ ተራ ነገር አይደለም፤ የአንዲት ሀገር ዜጎችን ጥርስ ለማናከስ በተንኮል የታቀደ ትልቅ ወንጀል ነው፡፡ በዚህ ደግሞ ማንም አይጠቀምም፡፡ ይህ የልቦለድ ታሪክ በአቶ ጃለታ የተፈለሰፈው ኦሮሞና አማራን በማጣላት ይገኛል ተብሎ የሚገመትን የሥልጣንና የኢኮኖሚ ጥቅም ታሳቢ ያደረገ የጎሣ ፖለቲካ ውጤት ነው፡፡ ከመነሻው ሚስተር ቡላቶቪችም ቢሆን ያን በአኀዛዊ ግምት ያስቀመጠውን የኢትዮጵያውያን ዕልቂት ሊደርስበት የሚያስቸለው አንዳችም የሕግ ድጋፍም ሆነ በግሉ የሚታወቅባቸው አቅምና ችሎታ የነበሩት ሰው አልነበረም፡፡ በሁለተኛም ያ ሰው የኦሮሞው ማኅበረሰብ ይኖርባቸው በነበሩ የኢትዮጵያ አካባቢዎች ዝኆንና ሌሎች የዱር እንስሳትን እያደነ በዛ ቢባል ለሁለት ወራት ያህል ብቻ ተዘዋወረ እንጂ ያን ከፍተኛ ወጪና የተማረ የሰው ኃይል የሚፈልግ የሕዝብ ቆጠራና የዕልቂት መንስኤ ጥናት ለማካሄድ የሚያስቸለው መደላድል በነዚያን በ1990ዎቹ ዓመታት ውስጥ ፈጽሞውን ሊኖረው አይችልም፡፡

ልቦለድ ቁጥር ሁለት፡-

“… አብዛኛው ሙስሊም የኦሮሞ ሕዝብ”

ሃቅ ቁጥር ሁለት፡-

ይህ ሐረግ በጥቂት የመገናኛ ብዙኃን አውታሮች ዘወትር ባይሆንም ካለፍ ካገደም የሚስተዋል ነው፡፡ በመሠረቱ በኦሮሞ ሃይማኖታዊ ታሪክ ከጥንት እስከዛሬ መቼም ቢሆን ‹አብዛኛው ሕዝብ እስልምናን ተከታይ ነው› የሚባል ሕዝብ ሆኖ አያውቅም፡፡ እንደእውነቱ ክርስትናም ሆነ እስልምና ከጊዜ በኋላ የመጡ እንጂ የአያት የቅድመ አያት ጥንታዊ ሃይማኖቶቻችን አይደሉም፡፡ ለምዕተ ዓመታት ስንከተላቸው የነበሩና በትውልድ ሲወራረሱ የቆዩ ሀገር በቀል ባህላዊ እምነቶች ነበሩን፡፡ (አሁንም ሊኖሩ ይችላሉ፡፡) ቀስ በቀስ ግን በተለይ የኦሮሞ መስፋፋት በተጋጋለባቸው ዓመታት እነዚህ ሁለቱ እምነቶች ወደኦሮሞው ሕዝብ ይበልጥ እየሠረጉ ገቡ፡፡ ሥርገቱም በፈቃዳችንና በተፅዕኖም እንደነበር ከታሪክ ድርሳናት እንረዳለን፡፡ በፈቃዳችን የሆነው እኛ በሰላምም ሆነ በጦርነት መልክ በሄድንባቸው የኢትዮጵያ ግዛቶች ውስጥ ከነበረው የክርስቲያን ወይም የሙስሊም ሕዝብ ጋር ስንዋሃድ ሲሆን በተፅዕኖ የሆነው እነዚሁ ኃይሎች የኛን ግዛቶች በሚወርሩ ጊዜ በሚያሳድሩት ተፅዕኖ ነው፡፡ የሆኖ ሆኖ ግን ያን ክስተት አሁን የኋሊት ዞረን ስናየው ጉዳዩ የሁለትዮሽ እንጂ በብቸኝነት አንደኛው ሃይማኖት በሌላኛው ላይ የበላይነትን የሚጭንበት ሁኔታ ስላልነበረ አንዱ ከአንዱ ጎልቶ የወጣበትና የኦሮሞን ሃይማኖታዊ ማንነት ቁልጭ አድርጎ የሚያሳይበት ሁኔታ አልተፈጠረም፡፡ በዚህ ረገድ አሁን እንኳን ብናይ በኦሮሞ ማኅበረሰብ ውስጥ ያለው የሁለቱ ሃይማኖቶች የተከታይ ብዛት ተካካይ እንጂ ያን ያህል አፍን ሞልቶ ሊያናግር የሚያስችል የቁጥር መበላለጥ የላቸውም፡፡ (የመጨረሻው የ2000 ዓ.ም የሕዝብ ቆጠራ እንደሚያሳየው 48 በመቶ የሚሆነው ኦሮሞ የ(ማንኛውም ዘርፍ) ክርስትና ሃይማኖት ተከታይ ሲሆን 47 በመቶው ደግሞ ሙስሊም ነው፡፡ እንደሚባለው ከሆነ ግን የእስልምና ሃይማት ተከታዩ ቁጥር በፍጥነት እያደገና በአንጻሩም የክርስትና ሃይማኖት እየጫጫ በመሄድ ላይ ያለ በመሆኑ በቅርብ ጊዜ ውስጥ በኦሮሞዎች ዘንድ የሙስሊም ማኅበረሰብ ቁጥር ከክርስቲያኑ ሊበልጥ እንደሚችል ከፍተኛ ግምት ተሰጥቶታል፡፡

ልቦለድ ቁጥር ሦስት፡-

“ሀበሾች ኦሮሞዎችን ለማንቋሸሽ አሉታዊ ትርጉም ባዘለ ቃል ‹ጋላ› እያሉ ይጠሯቸዋል፡፡”

ሃቅ ቁጥር ሦስት፡-

ይህን እብለትና ቅጥፈት የተሞላበትን የፈጠራ አባባል የሚጠቀሙበት ከፍ ሲል የተጠቀሱት መገንጠልን የሚያራምዱ የኦሮሞ ኤሊቶችና አጫፋሪዎቻቸው ናቸው፡፡ ይህን የሚያደርጉት በአባባሉ እውነትነት አምነው ሣይሆን በኦሮሞው ውስጥ የመረረ ስሜት ለመፍጠርና ሕዝቡ ሴማዊ ሀበሾችን(አማሮችን፣ ትግሬዎችንና ጉራጌዎችን) ፈጽሞ እንዲጠላ ለማድረግ ነው፡፡ ይህን በማድረጋቸው ቅራኔውን ያከረሩና በአቋራጭ የመገንጠል ዓላማቸውን ያሣኩ ይመስላቸዋል፡፡ የዚህ ቃል ጥንተ አመጣጥና ትርጉሙ ግን እንደዚህ ነው፡- ይህ አንቋሻሽ የሚመስል ‹ጋላ› የሚባል ቃል ለመጀመሪያ ጊዜ አገልግሎት ላይ የዋለው በዐረቦችና በሙስሊም ሶማሌዎች ሲሆን ኦሮሞዎችን ‹ጋል› በማለት መጥራታቸው በቃሉ ትርጉም መሠረት ኦሮሞዎች ‹ሃይማኖት የሌላቸው›ና ከነሱ የተለዩ ‹ባዕዳን› መሆናቸውን ለመግለጽ ነው፡፡ በኦሮሞ መስፋፋት ወቅት ሙስሊሞች በዚህ ቃል ኦሮሞዎችን መጥራት የፈለጉት ኦሮሞዎች የነበራቸው ባህላዊ ሃይማኖት/እምነት ከተለመደው የእስልምና ወይም የክርስትና ሃይማኖቶች የሚያፈነግጥ ሆኖ ስላገኙትና ያንንም በግዑዝ ነገሮች እንደማምለክ ወይም ከነአካቴው እንደሃይማኖት የለሽነት ስለቆጠሩት ነበር ተብሎ ይገመታል፡፡ እየቆዬ ግን ይህ አሉታዊ ፍቺ እንዲይዝ ጫና የተደረገበት ‹ጋላ› የሚል ቃል የኦሮሞን ማኅበረሰብ አባላት በቡድንም ይሁን በተናጠል ለመጥራት ሌሎች ኢትዮጵያውያንም ይጠቀሙበት ጀመር፡፡

ልቦለድ ቁጥር አራት፡-

“(በ19ኛው መቶ ክፍለ ዘመን መገባደጃ አካባቢ) ኦሮሞዎች በአፄ ምኒልክ ቅኝ አገዛዝ ሥር ወደቁ፡፡”

ሃቅ ቁጥር አራት፡-

የኦሮሞ ተገንጣይ ቡድኖች ከሚያናፍሷቸውና አንዳንድ የውጭ ጋዜጠኞችም በጭፍን ተቀብለው በተደጋጋሚ ከሚያራግቡላቸው የፈጠራ ወሬዎች መካከል አንደኛው አንድ ኢትዮጵያዊ ዘውግ (አማራ) ሌላውን ኢትዮጵያዊ ዘውግ (ኦሮሞን)በቅኝ ግዛት ሥር አስገብቷል የሚለው አስቂኝ ድራማ ነው፡፡ ይህ ጉዳይ ብዙውን ጊዜ “ሀበሾች ኦሮሞዎችን በቅኝ ግዛት ያዙ” ወዘተ. እየተባለ እንደመፈክር ይስተጋባል፡፡ ይህ የቅኝ ግዛት ነገር በኦነግና በመሰል የኦሮሞ ድርጅቶች እንዲሁም በአሜሪካና በአውሮፓ ሀገራት በሚገኙ የኦሮሞን ብሔርተኝነት አቀንቃኞች ዘንድ እንደእውነት ተወስዶ ለትግል ማነሳሻነትና ማነቃቂያነት ሲባል በስፋት ይወሳል፤ በሕዝብ ውስጥም ውስጥ ውስጡን ይሰበካል፡፡ በተለዬ አገላለጽና የዕይታ አቅጣጫ ሊታይ በሚችል መልኩ ይህ አንዱ ሌላውን ለመቆጣጠር የመሻትና የመሞከርም ሁኔታ ጨርሶውን ሊካድ ባይችልም … እንደአጠቃላይ ግን የኦሮሞ ብሔር መቼም ቢሆን በሌላ (የኢትዮጵያ) ዘውግ ቅኝ ተገዝቶ አያውቅም፡፡ ይህ ዓይነቱ ወሬ ሰሚን ሣይቀር ግራ የሚያጋባ ተራ ወሬ እንጂ ቅንጣት እውነትነት የለውም፡፡ በመጀመሪያ ደረጃ ሌላው ቀርቶ አንድ የተባበረ የኦሮሞ ብሔር፣ ተለይቶ ከሚታወቅ አንድ ወጥ የኦሮሞ ግዛት ጋር በነዚያ ሩቅ ጊዜያት አልነበረም፡፡ ፖለቲካዊ ተፅዕኖ የሌለባቸው የታሪክ መጻሕፍት ሁሉ የሚመሰክሩት አንድ እውነት አለ፡፡ ያም እውነት በኢትዮጵያ ውስጥ በሚገኙ ቋንቋቸው አንድ በሆነ ነገር ግን የተለያዩ የጎሣ/የነገድ ስብጥር ባላቸው ማኅበረሰቦች መካከል ለዘመናት ጦርነቶች መካሄዳቸው ነው፡፡ በልማዳዊ አነጋገር የ“ሀበሾች” ሥፍራዎች ናቸው በሚባሉ የሰሜን ኢትዮጵያ ብዙ ቦታዎች ሳይቀር ኦሮሞዎች በመስፋፋት ከትግሬዎች፣ ከአማራዎች፣ ከአፋሮችና ከሌሎችም የክልሉ ነዋሪዎች ጋር በመቀላቀላቸውና በመዋሃዳቸው ይህ በአንዳንድ የዋሃን “የሀበሾች ምድር” እየተባለ አላግባብ የሚጠራው የሰሜኑ የሀገራችን ክፍል ራሱ የአንዱ ወይም የሌላው ብሔር ወይም ዘውግ ብቸኛ መኖሪያ ሣይሆን የሁሉም እንደሆነ በታሪክ ምሁራን ዘንድ ይታመናል፡፡ እርግጥ ነው በ1700ዎቹ ገደማ ራያ ኦሮሞዎችና የጁ ኦሮሞዎች የተወሰኑ የትግሬና የአማራ ግዛቶችን ተቆጣጥረው በነበረበት ጊዜ ለተወሰኑ ዓመታት የኢትዮጵያን ኦፊሴል ቋንቋ ኦሮምኛ አድርገው እንደነበር ከታሪክ ማኅደር መገንዘብ ይቻላል፡፡ ይህም ማለት በኢትዮጵያ የተለያየ ቋንቋና ባህል ያላቸው ጎሣዎችና ነገዶች እየተፈራረቁ ሥልጣን ይናጠቁ እንደነበረና በታሪክ ግምዶሽ እየተቆራኙ እርስ በርስ እንደተዋሃዱ፣ በዚህ ሂደትም ይበልጥ ጉልበተኛ የነበረው ዘውግ ለአገዛዝ አመቺ ነው ብሎ የሚያስበውን ቋንቋም (ሆነ ባህል) በሌሎች ላይ ይጭን እንደነበር መረዳት አይቸግርም፡፡ የዚያን ዘመኑ የአንድ ቋንቋ የበላይነት ግን እንደዛሬው ዘመን አጨቃጫቂና ከመጠን በላይ በተለጠጡ የቅራኔና ቁርሾ መዘዞች የታጨቀ አልነበረም፡፡ ምክንያቱም በንግድም ሆነ በሌላ ሥራ ከቦታ ቦታ ይዘዋወሩ የነበሩ ዜጎች ለሥራቸው ስኬት ሲሉ በሚንቀሳቀሱባቸው አካባቢዎች የሚገኙ የሌሎች ጎሣዎችን ቋንቋዎች ይናገሩ ስለነበርና ቋንቋን ማወቅም ከግል ጥቅም ጋር በቀጥታ ስለሚያያዝ በዚያን ዘመን ይስተዋል የነበረው ሥነ ልሣናዊ ችግር እንዳሁኑ በፖለቲካዊ አስተሳሰቦች የተንኮል ድርና ማግ የተሸመነ አልነበረምና ያን ያህል ጎልቶ የሚታይ ለታሪክ መዝገብ ፍጆታም የሚበቃ ቋንቋ ነክ ችግር አልነበረም፡፡ ይህ እንግዲህ ኦሮሞ የሠፈረበትን ግዛት የሚጠቁመን የኋላ ታሪክ ነው፡፡ ታሪኩም የሚያሳየን ኦሮሞ ያልተዳረሰበት ኢትዮጵያዊ ሥፍራ እንደሌለና ነገር ግን በየሄደበት ባህልና ቋንቋ እየተዋጠ ከሁሉም ጋር እንደሰም ቀልጦ አንድ መሆኑን ነው፡፡ ወደኋለኛው የአፄ ምኒልክ ዘመን ስንመጣ እንግዲህ የሚስተዋል አንድ ሃቅ መኖሩን እንረዳለን፡፡ ይሄውም ብዙዎች የታሪክ ተመራማሪዎችና ጸሐፍት እንደሚከራከሩበትና አሳማኝም ነው ብለው በርካቶች እንደሚቀበሉት ጉዳዩ የአማራና የኦሮሞ ዝርያ ወይም የደም ትስስር ሣይሆን አማርኛን በዋናነት የሚናገር ማኅበረሰብ ኦሮምኛን በዋናነት የሚናገርን ማኅበረሰብ በጊዜ ሂደት ሊያሸንፍ የመቻሉ ታሪካዊ አጋጣሚ መከሰቱ ነው፡፡ ይህ ሲሆን አማርኛን በሚናገረው ማኅበረሰብ ውስጥ ኦሮሞ አለ፤ ኦሮምኛን በሚናገረው ማኅበረሰብ ውስጥም አማራ አለ ማለት ነውና ትግሉ ይበልጡን የኢኮኖሚና የሥልጣን እንጂ የዘርና የቋንቋ አለመሆኑን ልብ ይሏል፤ እርግጥ ነው ግጭቶች ሁሉ የሀሰትም ይሁን የእውነት አንዳች የሚነገርላቸው ምክንያት ስለሚያስፈልጋቸው በሁሉም ወገን የሚነገሩ ግን እውነት ውሸትነታቸው ሊጣራ የሚገቡ ሰበበ-ድርጊቶች መኖራቸው የሚካድ አይደለም፡፡ ጥንቃቄ የሚያስፈልገው እንግዲህ በነዚህ ዓይነቶቹ የኋላ ዳፋ ሊኖራቸው በሚችል ጠንቀኛ ንግግሮችና ሰብቆች ላይ ነው፤ ምክንያቱም ‹አንድ ወሬኛ ያባረረውን ሺ ጦረኛ አይመልሰውም› እንዲሉ ተጣሞ የተነዛን ወሬ ለማቃናት አስቸጋሪ ከመሆኑም በተጨማሪ ወሬው እየተበጠሰ እየተቀጠለ ይሄድና ያልተጠበቀ ከፍተኛ ችግር ይፈጥራልና ነው፡፡ ይህ ከፍ ሲል የተገለጸው የግጭትና አንዱ ሌላውን እያሸነፈ የማስገበር ሁኔታ የሚያመለክተን አማራ ኦሮሞን ወይም ኦሮሞ አማራን የማሸነፍ ጉዳይ አለመሆኑንና ታሪካዊ አንድምታው ከዚህ የፊት ለፊት ሽፋን ረቀቅ ያለና የተለዬ መሆኑን ነው፡፡ በተቻኮለ ፍርደገምድልነት የተሳሳተ አመለካከት ከማዳበር በፊት እውነትን መረዳት ለሁሉም ይጠቅማል፡፡
ሰሜነኞቹ አማሮች ጎራ ለይተው እንደተጋጩና ለጉዳት እንደተዳረጉ ሁሉ ኦሮሞዎችም እንዲሁ ጎራ ለይተው ግጭት ውስጥ ገብተዋል፡፡ ለዚህ አንዱ ግልጽ ማስረጃ የሚሆነን አፄ ምኒልክ በወጣትነታቸው ዘመን በአፄ ቴዎድሮስ ተይዘው ታስረው በነበረበት ወቅት በጎንደርና በሸዋ የአማሮች መኳንንትና መሣፍንት መካከል የታየው ፍጥጫ ነው፡፡ ወጣቱ ምኒልክ በተፈቱ ሰሞንም የኦሮሞ ነገዶች ኃይለኛ የርስ በርስ ውጊያ ላይ ነበሩ፡፡ የተቀናቃኞቻቸውን አከርካሪ በመምታት ያን ግጭት በአሸናፊነት ለመውጣት የፈለጉ የተወሰኑ የኦሮሞ ጦር ቡድኖች ከሸዋ አማሮች ንጉሥ አፄ ምኒልክ ጋር ኅብረት ፈጠሩ፡፡ ቱለማ ኦሮሞ፣ ሊሙና ሜጫ ኦሮሞ የሚባሉት የኦሮሞ ጦሮች ከሸዋው ንጉሥ ከአፄ ምኒልክ ጦር ጋር በመተባበር ሌሎችን የኦሮሞ ጦሮች በተለያዩ አስከፊ ዐወደ ዉጊያዎች በማሸነፍ ብትንትናቸውን አወጡት፡፡ ባጭሩ ኦሮሞዎች በኦሮሞነታቸው በአንድ ኦሮሞ ያልሆነ ባዕድ አካል በቅኝ ግዛት አልተያዙም፡፡ እርግጥ ነው የኦነግ መሥራች አባላት ይህን የ”ቅኝ ግዛት” ተረት ተረት ስላላመኑበት በተለይ በመጀመሪያ አካባቢ ይህን ያህል አፍ ሞልተው ሲናገሩት አልተስተዋለም፡፡ ይሁንና በ1960ዎቹ አካባቢ የኦነግ አመራሮች በግማሽ ኦሮሞ በሆኑት የወቅቱ የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት አፄ ኃይለ ሥላሴ ላይ ኦሮሞዎች እንዲያምጹባቸው ለማድረግ ስሜትን የሚማርክ አንዳች የመቀስቀሻ ዘዴ መቀየስ አስፈለጋቸው፡፡ ለዚያም ሲሉ ይህችን መናኛ የ‹ቅኝ ግዛት› ካርድ በማንሣት ‹ለኦሮሚያ ነጻነት› ሁሉም ኦሮሞ በትግሉ እንዲሣተፍና “ከኢትዮጵያ ቅኝ ግዛት” ራሱን ነጻ እንዲያወጣ ይቀሰቅሱበት ጀመሩ፡፡ በዚህ የኦሮሞ ነጻነት ግምባር ድንገተኛ የአቋም ለውጥ ምክንያት ከኢትዮጵያውያን ወገኖቻችን ጋር ለበርካታ ምዕተ ዓመታት በሁሉም ረገድ ተዋህደን እንዳልኖርንና በደምና በአጥንት እንዳልተሳሰርን ሁሉ እኛ ኦሮሞዎች “በማያውቁንና በማናውቃቸው አማሮች” አማካይነት እንደከብት በቅኝ ግዛት በረት ውስጥ የመገኘታችንን ምሥጢር ኦነግ ይፋ አደረገልን፡፡ ይህ ዓይነቱ የመጨረሻ ውራጅና ከተስፋ መቁረጥ የሚመነጭ የትግል ሥልት በሌሎች ሀገሮች ውስጥ በሚካሄዱ የነጻነት እንቅስቃሴዎችም ዘንድ ሥራ ላይ ሲውል ታይቷል፡፡ የኛን ሀገር ሁኔታ በሚመለከት አብዛኞቹ ኢትዮጵያውያን የሚረዱት ገሃዱ እውነታ ግን በታሪክ ጥንቃቄ የተሞላበት ልዩ ሙያ ተዳውረው የተሸመኑት የሸዋ አማሮችና ኦሮሞዎች ለዘመናዊት ኢትዮጵያ መፈጠር ዋና መንስኤ መሆናቸው ነው፡፡ “ሸዋዎች እነማን ናቸው?” በሚለው በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተጻፈ መጸሐፉ ላይ፣ የታሪክ ምሁሩና የሰው ዘር አመጣጥ ተመራማሪው ዶክተር ጌሪ ሳሎል ይህን የመሰለ ጠቅለል ያለ ድምዳሜ አስፍሯል፤ “ ዘር ቆጠራን በሚመለከት ሸዋ ውስጥ (ከዚያም በመላዋ ኢትዮጵያ) የፖለቲካ የበላይነትን የጨበጡትን ቡድኖች ብናይ ከአማራና ከኦሮሞ የተወለዱ ቅዩጣን ዜጎች ናቸው፡፡”
ወደማጠቃለያችን ስንመጣ እንግዲህ በዋናነት መገንዘብ የሚያስፈልገን ነገር ቢኖር ከፍ ሲል የተጠቀሱት አራት መሠረታዊ ስህተቶች የኦሮሞን ታሪክና ኦሮሞ በኢትዮጵያ የፖለቲካ ሕይወት የሚጫወተውን ሚና በሚመለከት መዘገብ የሚፈልጉ በተለይ የውጭ ሀገራት ጋዜጠኞችን በማሳሳትና እውነቱን እንዳይዘግቡ በማወናበድ እያደናቀፉ መሆናቸውን ነው፡፡ አልጀዚራን የመሳሰሉ ዕውቅ የመገናኛ ብዙኃን የኦሮሞንና የሌሎች ኢትዮጵያውያንን ችግርና እንግልት መዘገባቸው እሰዬው የሚያሰኝ መሆኑ እንዳለ ሆኖ ነገር ግን ያለባቸውን ኃላፊነት በብቃት ይወጡ ዘንድ ዘገባው ሚዛናዊ እንዲሆን ተጨማሪና ከፍተኛም ጥረት ማድረግ እደሚገባቸው መገንዘብ ይኖርባቸዋል፡፡ አለበለዚያ የሚሠሩት የተዛነፈ ሥራ በተለይ ወጣቱን ክፍል ወዳልተፈለገ አቅጣጫ ይመራውና ለችግሮች መፍትሔ ከማግኘት ይልቅ ችግሮች እየተባባሱ እንዲሄዱ ያደርጋል፡፡ እንደውነቱ ከሆነ በኢትዮጵያ ውስጥ እየመጡ በሚሄዱ የተለያዩ መንግሥታት አማካይነት ከፍተኛ የአስተዳደር በደልና ጭቆና የደረሰባቸውና የሚደርስባቸው ኦሮሞዎች ብቻ ሣይሆኑ ሁሉም ዜጎች ናቸው፡፡ ከዚህ አስከፊ የብረት አጥር ወጥተው ወደተሻለ የዴሞክራሲና የመልካም አስተዳደር ዘመን ሊሸጋገሩ የሚችሉት ደግሞ የጎሣና መሰል ልዩነቶቻቸውን ትተው ለጋራ መብቶቻቸው መከበር በአንድነት ሲቆሙና በአንድነት ሲታገሉ ብቻ ነው፡፡ በጋራ ሲሰለፉ ደግሞ የጋራ ጠላቶቻቸው በማር ለውሰው በመሃከላቸው በረጯቸው መርዘኛ አሉቧልታዎችና የሀሰት ወሬዎች መበርገግና በነጭ ውሸት የመሠሪዎች መሠረተቢስ ወሬ መረታት የለባቸውም – ‹ተደጋግሞ የተነገረ ውሸት እንደ እውነት ይቆጠራል› የሚባለውን ምሳሌያዊ አባባል በማስታወስ የሚነገረው ሁሉ እውነት እንዳልሆነ ማጤንና ሁሉም ትኩረቱን ከባርነት አገዛዝ ነጻ ወደሚያወጣው የጋራ መንገድ ማዞር ይኖርበታል፡፡ የውጭ የመገናኛ ብዙኃንም ያልተረጋገጠ የሀሰት ዘገባ በማቅረብ በሕዝብ መሀል ጥርጣሬንና መፈራራትን ከማንገሥ ተቆጥበው ትክክለኛነቱ በሁሉም ወገኖች ዘንድ የተመሠከረለትን ዘገባ ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል፤ ከዚህ ቀደም ኅትመት ወይም አየር ላይ ባዋሏቸው መሰናዶዎቻቸው ላይ ስህተት ካለም ጉዳዩ በቀጥታ ከሚመለከተው አካል ማስተካከያ መቀበልና ማስተላለፍ፣ ለቀደመ ስህተታቸውም ይቅርታን መጠየቅ ይገባቸዋል፡፡ እነዚህ ዓለም አቀፍ የሚዲያ ተቋማት ከአሁን በኋላ የኦሮሞ ማኅበረሰብ ከቀሪ ኢትዮጵያውያን ወገኖቹ ጋር ለዴሞክራሲ፣ ለልማትና ለፍትህ የሚያደርገውን ትግል የሚያደናቅፉ ከፋፋይና መሠረተቢስ ዝግጅቶችን ከማቅረብ እንዲቆጠቡ በዚህ አጋጣሚ ጥሪየን አስተላልፋለሁ፡፡

– ፈቃዱ ለሜሣ የናዝሬት ዩኒቨርስቲ የቀድሞ ፕሮፌሰርና ጸሐፊ ናቸው፡፡

ለማንኛውም አስተያየትና ሂስ የኔ አድራሻ፡- yinegal3@gmail.com
Original title of this translation:- History 101: Fiction and Facts on Oromos of Ethiopia
የኢትዮሚዲያ ምንጭ፡ Salem News
________________________________________
የኔ ምንጭ፡- Ethiomedia.com – An African-American news and views website.
Copyright 2012 Ethiomedia.com. Email: editor@ethiomedia.com

↧

በማሸበር የሚኖሩ በመግደል የሚከብሩ የሰው አረሞች

$
0
0

ዳኛቸው ቢያድግልኝtplf

አረም ማለት ያልተዘራበት የሚበቅል ገበሬ የዘራውን ሰብል የሚሻማ፣ ውሀውን የሚጠጣበት፣ ለበሽታና ተባይ መጠለያ በመሆን ለሰብል ጉዳት ምክንያት የሚሆን እጽዋት ማለት ነው። አረም በስሮቹ አማካይነት የሰብሉን ስር አንቆ የሚገድል፣ አንዳንዱም እንደ ፓራሳይት ሰብል ላይ ተጣብቆ የሚበቅል እንደ አቀንጭራ ያለ ማለት ነው። አረሞች በፈጣን አስተዳደጋቸው ሳቢያ አልሚ ንጥረ ነገሮችን ከመሬት የፀሀይ ብርሃን ከሰማይ በመሻማት የሚያቀጭጩና የሚገድሉ ናቸው። የስንዴ ማሳ ውስጥ የበቀለ በቆሎም እንኳ ቢሆን አረም ነው፣ ገብስም ቢሆን አረም ነውና ተነቅሎ ይጣላል።Tigray People Liberation Front Split

አረም ዘሩን በማባዛትና የመኖር እድሉን ለማራዘም በርካታ ዘዴዎችን እየተጠቀመ በብዛት የሚንሰራፋና በወቅቱ ካልታረመ ሰብል የሚያጠፋ ነው። ጎበዝ ገበሬ አርሞና ኮትኩቶ ሰብሉን ካልተንከባከበ በሰብል ምርት ምትክ አረሙን ማፈስ ይገደዳል። ልክ እንደ ምሳሌው ኢትዮጵያዊነትን የሰው አረም ውጦታል። ፀረ ኢትዮጵያና ኢትዮጵያዊነት አቋምን የያዘ በሌሎች ስም ይልቁንም በትግሬ ስም ኢትዮጵያዊነት ላይ ተጣብቆ አገር እያፈረሰ ያለ የዘራፊ ቡድን አገርና ሕዝብ እያቀጨጨ ነው። ወያኔ በቆሎና ማሽላ ላይ ተጣብቆ እንደሚበቅል አቀንጭራ (ፓራሳይት፣ ጥገኛ አረም) ኢትዮጵያዊነትን ተጣብቶ ኢትዮጵያን እየገደለ ያለ ቡድን ነውና ተነቅሎ መጥፋት አለበት። በምስሉ የተቀረጹ ‘ኦፖርቹኒስት’ ገንጣዮችና ከፋፋይ ድርጅቶችም እንዲሁ።

ስንዴ ማሳ ላይ የበቀለ ገብስ አረም የመሆኑን ያህል ኢትዮጵያዊነትን አቀጭጮ የሚገድል ኢትዮጵያዊም ቢሆን የሰው አረም ነውና ተነቅሎ ሊጣል ወይም ለፍርድ ሊቀርብ ይገባዋል። ምንጫቸው ትግራይ ስለሆነና የትግራይ ተገንጣይ ግንባር ነኝ ስላሉም የትግራይ ሕዝብ ውክልና የላቸውም። በመጀመርያ እኒህ የሰው አረሞች ጭካኔና ግድያን የተለማመዱት ኢትዮጵያዊነትን ከፍ ያደረጉ የትግራይ ተወላጆችን በማደን መሆኑን እናውቃለን። የታታሪ ገበሬን ምሳሌነት የመጠቀሚያ ጊዜው እየረፈደ ቢሆንም አረም ለማጥፋት በደቦ መጠራራት የመጨረሻው የመኖር ያለመኖር ተስፋችን ነው። እያዩ ማለቅንም እለት በእለት እየተለማመድነው ከብት ወደ መታረጃው እንደሚነዳው አቅመ ቢስነት ውስጥ ከገባን ያበቃልናል። ኢትዮጵያንና ኢትዮጵያዊነትን አምርረው በሚጠሉ ሰዎች ጥፋት ምክንያት ኢትዮጵያን ልንጠላ ግን አይገባም። ሰሞኑን ሰላማዊ ሕዝብ ላይ በሚደርሰው ጭፍጨፋ ኢትዮጵያዊነታቸውን እስኪጠሉ ድረስ የሚማረሩት ወገኖች ምሬታቸው ከፍቶ ሰው መሆናቸውን እስኪጠሉና የሚፈራውና ለብዙዎች ጥፋት ምክንያት የሚሆነው የአጥፎ መጥፋት እልቂት እስኪመጣ መጠበቅ ሞኝነት ነው።

በሀገራችን ገበሬው የአረም ማጥፊያ መርዝ የሚጠቀመው ጥቂቱ ነው። የገንዘብ አቅም ስለሚያንሰው መርዛማነቱም ለሌላው ስለሚተርፍ። ልክ እንደዚያው ወያኔን ለማጥፋት የድርጅት አቅም አንሶናል ወደ መሳርያ ማንሳቱ ሁሉም እየተገፋ ከመጣ ለብዙ ህይወት መጥፋትም ምክንያት ሊሆን ይችላል። ነገር ግን ገበሬዎች አረምን ለማጥፋት አንድ ግሩም ባህል አላቸው። ያም ደቦ፣ ጅጊ ወዘተ የሚባልና ተጠራርቶና ተሰባስቦ በህብረት ማሳቸውን ከአረም ማጽዳት የሚችሉበት መንገድ። ተመሳሳይ ብልህነት ከጠፋንና እያማረርን ዘመን ከቆጠርን ተራ በተራ አንዴ የተበደሉ ጎሳዎች አንድ ሰሞን፣ የተፈናቀሉ ወገኖች በሌላ ሰሞን፣ ክርስቲያኖች አምና እስልምና ተከታዮች ዘንድሮ፣ ሴቶች ትናንት፣ ወጣቶች ዛሬ ልላ እያልን በወረፋ መታረድን ልንለማመደው የግድ ይሆናል። አንዱ በሌላው ሞት ዝም በመሰኘት አጥፊዎቻችንን ጉልበት እየሰጠ፣ እነርሱም እየናቁንና እያፌዙብን በመጨረሻም አገር እንዲያሳጡን መፍቀድ የለብንም። ሕዝቡና የፖለቲካ ድርጅቶች ተበታትነው እየሮጡ ሲያልቁ የሰው አረሞች እየተሰፋፉና እየተመቻቸው መኖር የሚችሉበትን ሁኔታ እያመቻቹ የመቀጠል መዘናጋት ሊያበቃ ይገባል።

ዛሬ ያስቸገረንና የከበደን ሀገር በቀል አረም ነው ነገ ግን ጉልበተኛና ጨካኝ አንዴ እግሩን ከተከለ ማጥፊያ መንገድ የሌለው መጤ አረም ይውጠናል። በዚህ ከቀጠልን የዛሬዎቹ አረሞች ነገ ስማቸውን ለኛ ሰጥተውን እኛ እንደ አረም በመርዝ እናልቃለን። በዚህ ከቀጠልን ካሁኑ በከፋ ሁኔታ እንሰደዳለን እንሳደደለንም። ተቆጥቶ ለመነሳት በጣም አርፍደናል ባለቀ ሰዐትም እንኳ ቢሆን ለመነሳቱ ዛሬ ከነገ ይሻላል። ወያኔዎች በማሸበር የሚኖሩ በመግደል የሚከብሩና ሀገሪቱ የጦርነት ቀጠና ሆና እነሱ ወታደራዊ ስርዐትን አስፍነው ያሻቸውን እየገደሉ ለመኖር እየጣሩ ነው። አምባገነኖች ሁሌም በጦርነትና በቀውስ ሁኔታ ውስጥ መኖርን ይመርጣሉ። ምክንያቱም ሰላም ሲሆን እነርሱ መመለስ የማይችሉአቸው የመብት ጥያቄዎች ስለሚነሱ በስልጣን መቆየት አያስችላቸውም።

በፖለቲካ ድርጅትም ይሁን በጎበዝ አለቃ ሕዝቡ መንደሩን ሊያጸዳ ገዳዮቹን ለፍርድ ሊያቀርብ የሚችል ሀይል እንደሆነ ጠላቶቹ ሊያውቁት ይገባል። ተደጋግሞ እንደተገለጸው ወያኔ እርጉም ጠላት እንጂ መጥፎ መንግስት አይደለም። የሕዝብ ክብርና የሰዎች ነጻነትም አይገባውምና ተነቃቅሎ ሊጣል የሚገባው አረም ሊወገድ የሚገባው የሀገር ጠላት ነው።

ኢትዮጵያና ኢትዮጵያዊነት ከነፃነት ሰንደቅዓላማችን ጋር ለዘለዓለም ይኑርልን!

biyadegelgne@hotmail.com

↧

ግንቦት 7 “ሙስሊም ወገኖቻችን፤ ቁስላችሁን አስራችሁ ከወያኔ ጋር በምናደርገው ፍልሚያ ተቀላቀሉን”አለ

$
0
0

ginbot 7ግንቦት 7 ዛሬ ባወጣው መግለጫው ለመላው የሙስሊሙ ማህበረሰብ ጥሪ አቀረበ። ግንቦት 7 በመግለጫው “ሙስሊም ወገኖቻችን፤ ቁስላችሁን አስራችሁ ከወያኔ ጋር በምናደርገው ፍልሚያ ተቀላቀሉን!!!!” ሲል ጥሪውን አቅርቧል። ንቅናቄው ለዘ-ሐበሻ የላከው መግለጫ ሙሉ ቃል የሚከተለው ነው።
በእስልምና እምነት እጅግ በደማቅ ሁኔታ ከሚከበሩት በዓላት አንዱ የሆነው ኢድ አልፈጥር ለ1434ኛ ጊዜ ነሐሴ 2 ቀን 2005 ዓ. ም. በመላው ዓለም በደስታ ሲከበር ኢትዮጵያዊያን ሙስሊሞች ግን ለዚህ አልታደሉም። በእለቱ የኢትዮጵያ ሙስሊሞች የኢድ ሰላታቸውን ሰግደው ወደ የመኖሪያ ቤቶቻቸው ሲመለሱ ለድብደባ በሠለጠኑ የወያኔ ወታደሮች አሰቃቂ ሰቆቃ ተፈጽሞባቸዋል። በዚህ እለት በአዲስ አበባና እና ሌሎች ትላልቅና ትናንሽ ከተሞች በርካታ ወገኖቻችን ሕይወታቸውን አጥተዋል፤ አሁን ሕፃናት የወያኔ የጥይት ሰለባ ሆነዋል፤ ከዚያ እጅግ አሰቃቂ ግድያና ወከባ ያመለጡት ደግሞ የአካል ጉዳት ደርሶባቸዋል። በአስር ሺዎች የሚገመቱ ሙስሊሞች በዓሉን ያሳለፉት በወያኔ ማጎሪያዎች ውስጥ በሕመምና በረሀብ እየተሰቃዩ ነው።
ይህ ለምን ሆነ?
የኢትዮጵያ ሙስሊሞች በከፍተኛ የኃላፊነት ስሜት ጥንቃቄ የተሞላበት ተቃውሞ ሲያካሄዱ አንድ ዓመት አልፏቸዋል። እጅግ ጨዋ በሆነ መንገድ ላቀረቡት የመብት ጥያቄ በታላቁ በዓል ቀን ወያኔ የእንቢታ ምላሹን ወራዳ በሆነ መንገድ ሰጥቷል። ወያኔ ለሰላማዊ ተቃዉሞ ያለውን ንቀት እናቶችን፣ ሕፃናትንና አረጋዊያንን ጭምር በመደብደብ አሳይቶናል።
ግንቦት 7: የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ ሕይወታቸው ላለፈ ወገኖቻችን ቤተሰቦች መጽናናትን ይመኛል፤ የአካል ጉዳት የደረሰባቸውን ወገኖቻችን ሕመም ይጋራል። በባለጌ የወያኔ ወታደሮች የተገደለየ፣ የተረገጡ፣ በቆመጥ የተደበደቡ፣ የተሰደቡ፣ የተተፋባቸው ወገኖቻችን ሁሉ ሕመማቸውን ችለው፤ እልሃቸውን ውጠው ለመረረ ትግል እንዲዘጋጁ ግንቦት 7 ጥሪ ያደርጋል።
በሙስሊም ወገኖቻችን ላይ የደረሰው በደል በሁላችን ላይ የደረሰ ጥቃት፣ በደል ነው። የሙስሊም ወገኖቻችን የመብት ጥያቄ የኢትዮጵያዊያን ተበዳዮች ሁሉ ጥያቄ ነው። እነዚህ ጥያቄዎች በወያኔ አገዛዝ ሥር ምላሽ አያገኙም። ስለሆነም ተባብረን ኢትዮጵያችንን ከወያኔ ፋሽስታዊ አገዛዝ ነፃ አውጥተን ሁላችንም የነፃነት አየር Addis_august8_2013_16የምንተነፍስባት አገር እናድርጋት ዘንድ ዛሬውኑ የጋራ የትግል ጉዞ እንጀምር።
“ሙስሊም ወገኖቻችን ሆይ! እልሃችሁን ውጣችሁ፤ ቁስላችሁን አስራችሁ ከወያኔ ጋር ለሚደረግ ፍልሚያ ተቀላቀሉን!!!” በማለት ግንቦት 7፣ የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ ጥሪ ያደርጋል።
ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!!!
ግንቦት 7: የፍትህ፣ የነፃነትና የዴሞክራሲ ንቅናቄ

↧

ድምጻችን-ይሰማ፦ የመጀመሪያው በሳል ኢትዮጵያዊ ሰላማዊ ትግል (ከያሬድ አይቼህ)

$
0
0

ከያሬድ አይቼህ – ኦገስት 9፥2013

ህወሃት ደደብ ነው። ምንም የማይገባው ፡ ገደብ የማያቅ ፡ ግርድፍ ባዕዳዊ ድርጅት ነው። በአስተሳሰቡ ባዕድ ፡ በስነምግባሩ ባዕድ ፡ በግብረገቡ ባዕድ። ይሄን የህገ-አራዊት ድርጅት ፊት ለፊት የገጠመው የድምጻችን-ይሰማ ንቅናቄ ነው። የንቅናቄው ብስለት ፡ አርቆ አሳቢነት ፡ አገራዊነት እና ሰብዓዊነት ድንቅ ነው ፤ ድንቅ!

voice of peopleከ18 ወራት በፊት አካባቢ የጀመረው የድምጻችን-ይሰማ ንቅናቄን በመጠኑ ግራ በመጋባት እና በተደባለቀ ስሜት ስከታተል ቆይቻለሁ። በዩናይትድ ስቴትስ የምንኖር ሰዎች የአሜሪካንን ፊሪሃ-ኢስላም (islamophobia) ፕሮፓጋንዳ ሌት ተቀን ስለምንጋተው ፡ እኔም ፈሪሃ-ኢስላም ተጠናውቶኝ ነበር። “ለመሆኑ የኢትዮጵያ ሙስሊሞችም አሸባሪነትን ያስተናግዱ ይሆን?” የሚለው ጥያቄ በአይምሮዬ ጀርባ ሲያንዣብብ ቆይቷል።

ልጅ ኢያሱ መሃመድ አሊ (100 ዓመት)

የኢትዮጵያ ሙስሊሞች ታሪካዊ የሆነ የመንግስታዊ ተቋም ጫና እና ጭቆና እንደ ደረሰባቸው አምናለሁ። ልጅ ኢያሱ መሃመድ አሊን እንዳይነግስ ያገደው መንግስታዊ ፈሪሃ-ኢስላም ፡ በሌሎች ታሪካዊ ክስተቶችም ጫናውን እና ጭቆናውን ማሳየቱ የሚካድ አይደለም።

ሆኖም ግን አራዊቱ ህወሃት በ21ኛው ክፍለ ዘመን ፈሪሃ-ኢስላምን ተጠቅሞ መጅሊሱን (የኢትዮጵያ ሙስሊም ማህበርን) ለመቆጣጠር መፈለጉ ኢትዮጵያዊያን ሙስሊሞች አሁንም የመንግስት ተቋማዊ ጭቆና ቀንበር ፡ ከልጅ ኢያሱ መሃመድ አሊ ከስልጣን መባረር 100 ዓመት በኋላ ፡ ደግሞ መከሰቱ ሙስሊሞች መብታቸውን ካለስከበሩ ማንም እንደማያስከብርላቸው የሚያስረግጥ ሃቅ ነው።

የ18 ወራት ፈተና

ድምጻችን-ይሰማ ላለፉት 18 ወራት እንደ ወርቅ ተፈትኗል። መሪዎቹ ታስረዋል። ያልተለወጠው ነገር ቢኖር ግን የንቅናቄው ብስለት ፡ አርቆ አሳቢነት ፡ አገራዊነት እና ሰብዓዊነት ናቸው። ንቅናቄው በኢትዮጵያ ውስጥ ላሉ ለመብታቸው ለሚታገሉ ዜጎች ፡ ቡድኖች ፡ ድርጅቶች ሁሉ ትልቅ አርአያ ነው።

ሙስሊምየድምጻችን-ይሰማን አርአያነት በመከተል ሌሎች ንቅናቄዎች ህገመንግስታዊ መብቶች እንዲከበሩ ፋና ወጊ ሰላማዊ ትግልን ማራመዳቸው አይቀሬ ነው። የንቅናቄው ራሱን መግዛት ፡ ለአራዊቱ ህወሃት ወጥመዶች ራሱን አሳልፎ አለመስጠት ፡ በጽናት ጥያቄዎቹን በአርብ ጸሎት ላይ ማሰማቱ እጅግ ድንቅ ነው። ፍርሃት የማይበግረው ፡ የአውሬው ወያኔ ሚዲያ የማያግደው ፡ የሰላማዊ ትግል ጀግኖች ንቅናቄ በኢትዮጵያ ባለፉት 18 ወራት ተወልዷል።

የራሷ ሲያርባት የሰው ታማስላለች

አንዳንድ መሰሪ ፡ መርዛም ግለሰቦች የድምጻችን-ይሰማን ንቅናቄ “ለምን ለሁሉም ጥያቄ አይታገሉም?” የሚል የጥገኛነት ትችት ሊያሰራጩ ሲሞክሩ ፡ በተለይ ‘ሲቪሊቲ’ በሚባለው የፓልቷክ የዉሃ ላይ ኩበቶች ስብሳቤ ክፍል አዳምጫለሁ። ለራሴ ነፃነት ሃለፊነቱ የእኔ ነው።

በዲያስፓራ ተቀምጠን ፊትለፊት ያለምንም ፍርሃት አራዊቱን ወያኔ የሚጋፈጡትን የሰላማዊ ታጋዮች መተቸት የሞራል ዝቅጠት ፡ የስነልቦናን ውርደት እና የሰብአዊነት ኪሰራን የሚያሳይ ነው። የዲያስፓራ ቱልቱላዎች እረፉ። ባታርፉም ምንም ስለማታመጡ እረፉ።

ድምጻችን-ይሰማን መቃወም አራዊቱን ወያኔን መደገፍ ነው። ፈሪሃ-ኢስላም ያላችሁ ሰዎች ፡ የድምጻችን-ይሰማን የትግል መስመር ፡ ፈተና እና ጽናት ብታጤኑ እንደ እኔ ከፍርሃታችሁ ነጻ ትወጣላችሁ።

ድምጻችን-ይሰማ ግፋ! ቀጥል! በአላማህ ጽና!

ክብር ለሰማዕታት!

ኢድ ሙባረክ።

- – -
አድራሻ፦ yared_to_the_point@yahoo.com

↧
↧

ከፖለቲከኞች በላይ ገኖ የወጣው “ድምጻችን ይሰማ”

$
0
0

በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

ኢህአዴግ አክራሪነትን እየጋበዘ ነው!!

dimpoli

”የሰላማዊ ትግል ምንነት ለማይረዱ ትልቅ ትምህርት የሰጠ፣ ኢህአዴግ ፍጹም የሆነ ልምድ ባካበተበትና ኤክስፐርት በሆነባቸው የትግል ስልቶች ብልጫ ወስዶ ለማንበርከክ እንደሚያስቸግር፣ ሰላማዊ ትግል ከራስና ከስሜት ጋር የሚደረግ ታላቅ አስተምህሮት መሆኑን ለማረጋገጥ ተችሏል። የድምጻችን ይሰማ ትግል በዚህ መልኩ በኢትዮጵያ ቀዳሚ ሆኖ ይቆያል” በግል አድራሻ ከተላከ አስተያየት የተወሰደ።

በአሃዝ፣ ጉዳቱ በሚገለጽበት መጠን፣ ጉዳቱ የሚገለጽበት ደረጃና የቋንቋው አቅም ልዩነት ካልሆነ በስተቀር ሁሉም ወገኖች፣ የውጪ ታዛቢዎች፣ በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ ጉዳዩ የሚመለከታቸው አካላት፣ ራሱ ኢህአዴግ፣ ህወሃትና መላው ወዳጆቹ በአንድ እውነት ይስማማሉ። እሱም ህወሃት ራሱ ባመጣው ጣጣ፣ ራሱ ትዕዛዝ ሰጪ ሆኖ ያደረሰው ሰብአዊና በቀላሉ ሊበርድ የማይችል መከራ እንደሆነ በየአቅጣጫው አስተያየት እየተሰጠ ነው።

ያለ ምንም ማጋነን ኢህአዴግ ደም አፍሷል፣ ህይወት ቀጥፏል፣ አስሯል፣ ገርፏል፣ ፈንክቷል፣ ጣጣው ለሌሎች የሚተርፍ አካሄድ በመከተሉ ችግሩን አወሳስቦታል። ኢህአዴግ ይህንን ሁሉ ርምጃ የሚወስደው “ከብዙ ትዕግስት” በኋላ መሆኑን “በመንግሥት ወግ” ቢገልጽም “የሚያምነው ያገኘ አይመስልም” የሚል ወቀሳም ይሰነዘርበታል። እንደውም “ለየትኛዋ የሚወዳት አገር” በሚል ለፕሮፓጋንዳ አፉን በከፈተ ቁጥር ዘለፋ እየወረደበት ነው።

“ኢህአዴግ ጉልበት አልባ ተደረገ!”

ኢህአዴግ አቅም አልባ ሆኗል የሚሉ ወገኖች አሉ። እነዚህ ወገኖች ገለጻቸው ለሌላው ግራ የሚያጋባ አባባል ሊሆን እንደሚችል ይገምታሉ። ግን በነሱ እምነት ኢህአዴግ አቅም አልባ ሆኗል። አቅም አልባ ያደረገው “የድምጻችን ይሰማ” የትግል ስልት ነው። ኢህአዴግ ያለውና 4የሚታወቅበት መለያው የታጠቀው መሳሪያ፣ ወታደሩ፣ የፌደራል ሃይሉ፣ የክልል ፖሊስ፣ ፈጥኖ ደራሹ፣ የሰላምና መረጋጋቱ ፣ የስለላ ሃይሉ፣ የአጋዚ ጦሩ፣ የአንድ ለአምስት አወቃቀሩ … ከሁሉም በላይ ደግሞ ጉልበተኛነቱን የሚቆጣጠሩለት የአንድ ብሔር “ታማኝ” ሃይሎች መሆናቸው እንደሆነ አብዛኞች ይስማማሉ።3

“ኢህአዴግ አለኝ የሚለውን ጉልበቱን መጠቀም ቢፈልግም መድረኩን ‘በተጠና’ የትግል ስልት በሚፈልገው ደረጃ ሊጠቀም አለመቻሉ በደጋፊዎቹና በራሱ ዘንድ ስጋት ፈጥሯል” የሚሉት አስተያየት ሰጪ “የሙስሊሞች እንቅስቃሴ፣ የዕዝ ሰንሰለታቸውን ጠብቀው የሚያካሂዱት ትግል ኢህአዴግ ጉልበቱን እንዳይጠቀም ከልክሎታል። አሁን እየወሰደ ያለውና የወሰደው የሃይል ጥቃት ሊወስድ ከሚፈልገው ጋር ሲነጻጸር ሃይሉ ሽባ መደረጉን ያሳያል፤ ይህ ደግሞ የሰላማዊ ትግል ውበት ነው” ሲሉ ኢህአዴግ በገባው ጭንቅ መጠን ርምጃ ባለመውሰዱ እንደሚቆጭ ይናገራሉ። በሌላ አነጋገር የሽብር፣ የማሸበርና የመግደል “ጠቢብ” ለሆነው ኢህአዴግ አሁንም ችግሩ የሚፈታው በሃይል፣ በባሰ ሃይል እንደሆነ ከማመን አላፈገፈገም ሲሉ ያብራራሉ።

ኢህአዴግ ነገሮችን እያባባሰ የሰላማዊ ትግሉን ወደ አመጽ ለማስቀየር ሃሳብ ቢኖረውም “የድምጻችን ይሰማ ህብረት አስቀድሞ መረጃ የማግኘትና በሰላማዊ ትግል ተክኖ መገኘት ኢህአዴግ ያሰበውን እንዳይፈጽም አድርጎታል” በማለት አስተያየታቸውን ይሰጣሉ። እነዚህ ክፍሎች ኢህአዴግ “አክራሪነትን የሚሰብኩና የሚያቀነቅኑ አሉ” በማለት ለሚለፍፈው “እስካሁን የአክራሪ ሙስሊም እንቅስቃሴ ስለመታየቱ መረጃ የለም። ከተፈጠረም አክራሪነት እንዲፈጠር ምክንያት የሚሆነው ራሱ ኢህአዴግ ነው። ደም ማፍሰሱን አጠናክሮ በቀጠለና ዜጎችን ማሰሩ በገፋበት ቁጥር ለመሞት የሚዘጋጁ ዜጎች አገር ውስጥ የመኖራቸውን ያህል የወንድሞቻቸውን ጭፍጨፋ በመመልከት የመስዋዕትነቱ ተካፋይ ለመሆን ዓለምአቀፋዊ የሙስሊም ኅብረተሰብ ቁጣ ያስተባብርና ራሱን ችግር ላይ ይጥላል፤ ለአገርም መከራ ይሆናል፡፡”

በተቃራኒው አክራሪነት እየተስተዋለ የመጣው አሁን እንዳልሆነ የሚናገሩ ክፍሎች “በአሁኑ ሰዓት አገራችን ውስጥ ያለው የሃይማኖት ውህደት ቀደም ሲል እናቶቻችንና አባቶቻችን በየዋህነት ሲያደርጉት እንደነበር አይነት ነው ብሎ ማሰብ የዋህነት ነው” በማለት ይናገራሉ። በማያያዝም እንዲህ ያለው ስጋት በሰላማዊ ትግል ጉልበት አልባ የሆነውን ኢህአዴግ ሃይል እንዲያገኝና ይህንን ሃይል እንዲተማመን አድርጎታል ሲሉ ይከራከራሉ።

“ኢህአዴግ ሰክሯል”

ኢህአዴግ መስከሩን፣ አንጎሉ መዞሩንና የሚያደርገው እንደጠፋው የሚናገሩ ክፍሎች እንደሚሉት የኢድ ቀን ኢቲቪ ያሰራጨውን ዜና ቀላል ምሳሌ አድርገው ያቀርባሉ። የድምጻችን ይሰማ መነሻ ምክንያት የሆኑትን አዲሱን የመጅሊስ መሪ በቴሌቪዥን መስኮት አቅርቦ 2“ሙስሊሞች ላይ የወሰዳችሁትና የምትወስዱት ርምጃ የሚደገፍ ነው፣ ትክክል ነው” በማለት ያቀረበው ቃለ ምልልስ “ከስካርም በላይ አዙሪት ነው” ሲሉ የኢህአዴግን የበሽታ መጠን ይገልጻሉ። ሙስሊሙን አንኳን አሰራችሁት፣ ደበደባችሁት፣ ገደላችሁት በሚል ደረጃ “ደግ አደረጋችሁ፣ ርምጃችሁ ትክከል ነው” በማለት ዜና ማሰራጨቱ ኢህአዴግ በራሱ ሚዲያ በችግሩ ላይ እሳት ማርከፉን የሚያመላክት  ስለመሆኑ በማሳያነት ያቀርባሉ።

አንድ ጤና ያለው መንግስት የህዝብ ቁጣ ሳይለሳለስ፣ የቁጣውን መንስዔ አደባባይ በማቅረብ “ተጎዳን በሚሉ የህብረተሰብ፣ በተለይም የአንድ እምነት ተከታዮች ፊት ማዘፈን ኢህአዴግን የያዘውን የስካር የዞረ ድምር  (ሃንግኦቨር) የማሽተት ያህል ነው” የሚሉት ክፍሎች ኢህአዴግ ቢያንስ ለራሱ፣ ህወሃትና ቁንጮው ላይ ሆነው ሃብት ለሰበሰቡት ሲል እርቅ ሊወርድ የሚችልበትን መንገድ እንዲያስብበት ይመክራሉ። ጉዳዩንም በጥበብ እንዲይዘው ይመክራሉ።

መተማመን ድሮ ቀረ!!

በሙስሊም ወገኖች አወሊያ የተጀመረው የድምጻችን ይሰማ ጥያቄ፣ የኢህአዴግ የጥያቄው አያያዝ ችግር ተዳምሮበት የእምነቱ ተከታዮች ባሉበት ቦታ ሁሉ ተቃውሞው እየተዳረሰ ይገኛል። የአገሪቱን ሙስሊሞች ከጫፍ እስከጫፍ በሚያስገርም የግንኙነት መረብ እያስተባበረ የሚነደው ሰላማዊ ቁጣ የሌሎች እምነት ተከታዮችን ድጋፍ አለማግኘቱን ለኢህአዴግ ሃይል እንደሆነው የሚናገሩ ወገኖች “ይህንን አስመልክቶ በሚቀርበው መረጃ ግራ ተጋብተናል” ይላሉ።

“እንኳን የሌላውን ሃይማኖት የራሳቸውን ሃይማኖትና ስርዓት ማስጠበቅ ያቃታቸው የክርስትናው ሃይማኖት ተከታዮች፣ የሙስሊሙን እንቅስቃሴ ደገፉ ተብሎ ሲዘገብ ዘገባው ሚዛን የሚደፋ አይሆንም” በማለት የሚከራከሩ ክፍሎች “የክርስትና እምነት ተከታዮች ለእምነታቸው ሊሰጡ የሚገባውን ክብር ከድምጻችን ይሰማ እንቅስቃሴ መማር ከቻሉ ይህ ብቻ በራሱ ይበቃል” በማለት በተቃራኒ ወቀሳ ይሰነዝራሉ። እንደውም የራሳቸውን የእምነት ቤት ማጽዳት ባለመቻላቸው ሊወቀሱ እንደሚገባ መረጃ በማጣቀስ ይከራከራሉ።

በሌላ በኩል ኢትዮጵያ ላይ ካለው የረዥም ጊዜ የተቀነባበረ ሴራና የምንገኝበት የጂኦ ፖለቲካ ካሸከመን ጣጣ ጋር በማዳመር “ሜዳዎች ሁሉ ሸራተን ሆነው አይዋቡም” የሚል አስተያየት የሚሰጡ ክፍሎች “መተማመን ድሮ ቀረ” ሲሉ የሌሎች እምነት ተከታዮችን ዝምታ ይገልጹታል።

“ሙስሊሞች አብዛኞች በሆኑበት ቦታ ያለ ችግር ቢፈልጉ አክርረው፣ ቢፈልጉ አለዝበው እምነታቸውን ያራምዳሉ። አነስተኛ በሆኑባቸው አገራት ደግሞ ያለውን የአስተዳደር መሰረት የመጋራት ፈተና ይፈጥራሉ”  የሚሉት እነዚህ ክፍሎች “እነዚህ በሌሎች አገሮች የታዩ ተሞክሮዎች ከምዕራቡ መገናኛ ውስወሳ ጋር ተዳምረው በክርስትና ሃይማኖት ተከታዮች ላይ ያስቀመጡት ጠባሳ ቀላል አይሆንም። ኢትዮጵያ ውስጥም ይህ ችግር አለ” ባይ ናቸው። በሌላም በኩል በማህበራዊ ድረገጾች አርሲ አርባ ጉጉና ጅማ የተከናወነውን በማንሳት ሰሞኑንን ለመከራከር የሞከሩትን በመጥቀስ የፍርሃቻው ማሳይ አድርገው ያስቀምጡታል።

ፍጹም ሰላማዊ ትግል – ፍጹም የሚያስቀና ህብረት!!

መሰረታዊ የእምነትና አመራር ጥያቄ በማንሳት ትግላቸውን በተጠና መንገድ የሚያካሂዱት የ”ድምጻችን ይሰማ” የትግል መስመር አስገራሚ እየተባለ ነው። ህብረታቸውና በተዋረድ የሚያካሂዱት መናበብ አስደማሚ ሆኗል። አልፎ አልፎ ከሚሰራጩ ወፍ ዘራሽ5 መልዕክቶች በስተቀር መሪዎችን በመከተል የሚያሳዩት ትብብር የሚያስቀና እንደሆነ እየተነገረ ነው። ተመሳሳይ ዓላማ ይዘው እርስ በርስ የሚቧቀሱት የተቃዋሚ የፖለቲካ ሃይሎች ከድምጻችን ይሰማ “የሰላማዊ ትግል” ቀመር ሊማሩና ይሁንታ ካገኙ ስልጠናም ሊወስዱ እንደሚገባ የሚናገሩ ተበራክተዋል።

እነዚህ ወገኖች እንደሚሉት የሙስሊም ወገኖች ጥያቄና ጥያቄያቸው መልስ ካላገኘ ወደኋላ እንደማይሉ በመደጋገም ይፋ እያደረጉ ነው። ኢህአዴግ ከተካነበት ድርጅቶችን የመሰንጠቅና “የእባቡን አንገት ቁረጥ” ከሚለው የአምባገነኖች መርሁ አንጻር ድምጻችን ይሰማ ውስጥ ዘልቆ መግባት አለመቻሉ አስገራሚ የሆነባቸው ጥቂት አይደሉም። ቅንጅት እንደ ሰደድ እሳት አገር አዳርሶ ኢህአዴግን ባስጨነቀ ማግስት “ሳሎኑ ተበርግዶ ኢህአዴግ ሲንቦጫረቅበት” የተመለከቱ፤ ዓመት ከመንፈቅ ያህል የዘለቀውንና ከዕለት ወደ ዕለት በብቃትም ሆነ የኢህአዴግን መሠሪነት በመመከት እንዲሁም የተጠና የትግል ችሎታ በማሳየት ወደር ያልተገኘለትን የድምጻችን ይሰማ ትግል ከማድነቅ ወደኋላ አይሉም። ለሌሎች ሲመክሩም የመስመርና የትግል አስተላለፍ ለውጥ ለማድረግ አሁንም ጊዜው እንዳላለፈ ሊገነዘቡት ይገባል በማለት ለሌሎች የሰላማዊ ትግል ምንነት ላልገባቸውና የገባቸው መስሏቸው ተስፋ ለቆረጡ ይመክራሉ፡፡

ማስታወሻ

ይህ ሪፖርታዥ የተቀናበረው የዝግጅት ክፍላችን ካነጋገራቸው ወገኖችና በኢሜል ከተላኩ መልክዕክቶችና አስተያየቶች በመመርኮዝ ነው። ለንባብ እንዲያመች የአርታኢ ስራ ከመሰራቱ ውጪ ሙሉ ሃሳቡ የተለያዩ አስተያየት ሰጪዎች ያሰፈሯቸው ነው። አሁንም በዚህ ጽሁፍ ላይ የቀረቡትን ሃሳቦች በማስፋትም ሆነ በመቃወም የሚላኩ ጽሁፎችን ለማስተናገድ ዝግጁ ነን። (ፎቶዎቹ የተወሰዱት ከቢላል Tube Photos ድረገጽ ነው)

↧

በረመዳን ደም ዕምባ! በየጐንቻው!

$
0
0

Download (PDF, 562KB)

<script type=”text/javascript”><!–
google_ad_client = “ca-pub-8555893555560582″;
/* Add 468 x 60 – Banner */
google_ad_slot = “5735223818″;
google_ad_width = 468;
google_ad_height = 60;
//–>
</script>
<script type=”text/javascript”
src=”http://pagead2.googlesyndication.com/pagead/show_ads.js”>
</script>

↧

የሽብርተኝነት ምንጭ ጭቆና ነው!

$
0
0

Abrham Destaደርጎች ‘ወንበዴዎች’ አሉን፤ ኢህአዴጎች ‘አሸባሪዎች’ አሉን። ያው ነው፤ ገዢዎች ለስልጣናቸው አስጊ የሆነ ሰው (ወይ ቡድን) ሲያጋጥማቸው ስም ሰጥተው የማጥላላት ዘመቻ ያካሂዳሉ።

የማጥላላቱ ዘመቻ ዋና ዓላማ ለስልጣን ስጋት የሆኑ ሰዎች ከህዝብ ለመነጠል ነው፣ ድጋፍ እንዳያገኙ ለማድረግ።

ግን ‘ወንበዴዎች’ ወይ ‘አሸባሪዎች’ እንዴት ይወለዳሉ? እንዴትስ ያድጋሉ? የውንብድና ወይ ሽበራ ምንጭ ጭቆና ነው። የጭቆና ምንጭ አምባገነንነት ነው። አምባገነንነት በሰው ህይወት፣ አስተሳሰብና ሃይማኖት ጣልቃ መግባት ይጨምራል።

ሰው ለመግዛት ጣልቃ መግባት የህዝቦች ነፃነት ማፈን ያመጣል። የሰዎች ነፃነት ማፈን የህዝቦች መብት መጣስ ነው። ህዝቦች መብታቸው ሲጣስ መብታቸውን የሚስያከብሩበት መንገድ ያፈላልጋሉ።

መንግስት በማይፈቅደው መንገድ መብታቸው ለማስከበር ሲንቀሳቀሱ ‘ሕገወጥ’ ተብለው ‘ወንበዴዎች’ ወይ ‘አሸባሪዎች’ ይሰየማሉ። መንግስት ‘ሕግ ለማስከበር’ በሚል ሰበብ የሃይል እርምጃ ይወስዳል። መጀመርያ ሕግ የጣሰ አካል ግን መንግስት ነው፣ የዜጎችን መብት በመጣስ። እናም ችግሩ እየተባባሰ ይሄዳል። ከተባባሰ ደግሞ የሃይል ሚዛን እንጂ የመደገፍና መቃወም ጉዳይ አይሆንም።

ስለዚህ ውንብድና ወይ ሽበራ የሚወለደው ከጭቆና ሲሆን የሚያድገውም በመንግስታዊ ያልተፈለገ የሃይል እርምጃ ነው። መንግስት በያዘው መንገድ ከቀጠለ ሀገራችን ወዳልተፈለገ የብሄርና የሃይማኖት ብጥብጥ ልትገባ ትችላለች።

መንግስት ችግሩ የመፍታት ግዴታ እንጂ የማባብስ መብት የለውም። አሁን እየተወሰደ ባለው የሃይል እርንጃ ምክንያት ብዙ ሙስሊሞች ሳያስቡት ወዳልተፈለገ በሃይል መብትን የማስከበር ተግባር ሊገቡ ይችላሉ። በደርጋዊ እርምጃ ምክንያት ብዙ የትግራይ አርሶአደሮች ሳያስቡት ከህወሓት ጎን ተሰልፈው ለመዋጋት ወስነው ነበርና።

የሙስሊሞች ጉዳይ መፍትሔ ይሻል። ከሃይማኖት አልፎ የሀገር ጉዳይም ነው።

የሽብርተኝነት ምንጭ ጭቆና ነው። ስለዚህ ሽብተርኝነትን ለመዋጋት ምንጩ ማድረቅ አለብን፤ ጭቆናን መዋጋት አለብን። የሃይል እርምጃ ሽብርተኝነትን የሚያባብስ እንጂ የሚፈታ አይደለም።

It is so!!!

↧

ተሸንፈን እንዳንቀር (ሉሉ ከበደ)

$
0
0

(ሉሉ ከበደ)

Commentአንባ ገነኖች ስልጣን ላይ የሚቆዩበት ጊዜ እየረዘመ በሄደ ቁጥር አሰራራቸውን እየገመገሙና ራሳቸውን እያረሙ፤ ስልጣን ላይ ለመዝለቅ ያበቋቸውን ስልቶች የበለጠ ማጠናክራቸው እንዳለ ሆኖ፤ ቆይታቸው አዳዲስ ስልቶችን ለመፍጠርና ለመሞከርም እድል ይሰጣቸዋል ። ለምሳሌ መለስ ዜናዊ አባይን እንገነባለን  ብሎ ድንገት  እየተጯጯኽ  ህዝብን ማሯሯጥ እንደጀመረው አይነት።

ይህ አባይን የመሰለ ብሄራዊ ጉዳይ ባልታሰብ ሁኔታና ጊዜ ድንገት ያነሳው ቡድን፤ ኢትዮጵያን እንደሀገር ሊያቆዩአት የሚችሉ ልዩ ልዩ ብሄራዊ ጥቅሞችን ለባእዳን አሳልፎ የሰጠ፤ ብሄራዊ እሴት ከኢትዮጵያዊ ብሄራዊ ስሜት ጋር እንዲጠፋ የሚታገል፤ በኢትዮጵያ ህዝብ ምኞት ቁማር ተጫውቶ ወደ ኢትዮጵያ ትመጣ ይሆናል  ያላትን የአረብ አብዮት ሊያሳልፍ እንጂ የሚጠላውን የኢትዮጵያ ህዝብ  ሊጠቅም አባይን እንደማይገነባልን እናውቀዋለን።

የኢትዮጵያ ህዝብ  የሚሾመው፤ የሚሽረው፤ የኔ የሚለው መንግስት ሲኖረው፤ በብሄራዊ ኢትዮጵያዊ ስሜትና አንድነት፤ በሀገር ፍቅር ስሜት ተገንብቶ የተደራጀ ብሄራዊ ጦር ሲኖረው፤ በሙያው የተካኑ የሀገር ልጆች ተሰብስበው፤  ከመንግስታቸው፤ ከህዝባቸው ጋር መክረው፤ የግንባታውን አይነትና መጠን ሰፊ ጥናት አካሂደው፤ በየትኛው ቦታ፤ መቼ፤ እንዴትና ለምን አላማ  በምን መጠን ብንገነባው በህዝቡ ኑሮ ላይ ቀጥተኛ ለውጥ ሊያመጣ የሚችል ትርፍ ያስገኛል  ብለው መክረው፡ በውትድርናውም በህጉም አቅጣጫ ሊከተል የሚችለውን ሁሉ  አጥንተው፤ ገምተው፤ ሁሉም ዝግጅት ከኢትዮጵያ ህዝብ ጋር ተደርጎ አባይ ለኢትዮጵያ በኢትዮጵያውያን ሊገንባ ይችላል። የኢትዮጵያ ህዝብ በማናቸውም መልኩ፤ የሚከፈለውን መስዋእትነት ከፍሎ ሊያስወግደው የሚገባ ጠላት፤ አባይን ከኢትዮጵያ ህዝብ በሰረቀው ገንዘብ ለመገንባት ፍቃደኛ ቢሆን  እንኳ ህዝቡ ባንድ እጁ ወንዙን እየገደበ ባንድ እጁ እየታገለ ሀገሪቱንና ራሱን ነጻ ማውጣት አለበት። ወያኔ በኢትዮጵያ ውስጥ የሚያደርገው ነገር በሙሉ በራሱ ጥቅም ዙሪያ የተሰላ እንጂ ለህዝብና ለሀገር ይጠቅማል ተብሎ አይደለም።

አለቃቸው ከሞተ በኋላም የተረፉት የወያኔ መሪዎች፤ ሌጋሲው እያሉ ህዝቡን ማደናቆርና የዘረፋና የስርቆት እስትራቴጂአቸውን ማጠናከሩን ቀጥለዋል። ሌጋሲ ጥሎ አለፈ የሚባለው መሪ፤ እንደ ኒልሰን ማንዴላ፤ ህይወቱን ሙሉ ለሰው ልጆች አንድነትና እኩልነት ሲታገል፤ ጥቅሙንና ህይወቱን ለመስዋእትነት አቅርቦ፤ ሀገር ለበቀሉባት ዜጎቿ ሁሉ እኩል መኖሪያ እንድትሆን፤ እኩል ሀብት እንድትሆን፤ ዜጎች በዘርና በቀለማቸው አንዱ ከፍ አንዱ ዝቅ ሳይል እኩል አይን ለአይን እየተያዩ እንዲኖሩ የሚያስችል ስርአት እንዲሰፍን አድርጎ የሚያልፍ መሪ ነው። እንደመለስ ዜናዊ አይነት በዘረኝነት የቆሸሸ፤ ያንኑ ካንሰሩን ህዝብ ላይ አራግፎ በሰላም የኖረን ህዝብ እንዲበጣበጥ አድርጎ የሞተ ሰው ጥሩ ሌጋሲ ሳይሆን ጊዜ ጠብቆ የሚፈነዳ ቦንብ በህዝብ መካከል ቀብሮ  አለፈ ነው የሚባለው። መሰረትና ምክንያት ከሌለው በቀልና ጥላቻ ጋር ተወልዶ፤ አማራ የሚባል ዘር ጨፍጭፎ ሳይጨርስ እግዚአብሄር ፍርዱን የሰጠውን ሰው፤ በተጨባጭ ሲጨፈጭፉት፤ ሲያስሩት፤ ሲያግዙት፤ ለኖሩት ነጮች ምህረት አድርጎ፤ ትውልድን አስታርቆ፤ ሰላም አውርዶ፤ የአምላክን ሚና ለተጫወተ ታላቅ ሰው ማንዴላ የሚገባውን ክብር ለወያኔ ቆሻሾች መዘከር በህዝብ ማላገጥ ነው።

እንደ ወያኔ አይነት የህዝባቸውንና የሀገራቸውን ጥቅም ለሌላ አገር ህዝብና መንግስት አሳልፎ ለመስጠት የተዘጋጁ ወገኖች ባሉበት ሀገር  እነዚህ ገዢዎች የተወዳጇቸው መንግስታት የጥቅም ቁርኝታቸውን ዘላቂነት ለማረጋገጥ በስልጣን ላይ እንዲዘልቁ የበኩላቸውን ምክር  መለገሳቸው የማይቀርና የተለመደ ነገር ነው። ባእዳኑ  ማናቸውንም የረቀቀ የአፈናና የጭቆና ዘዴ ስለሚመክሯቸው ስለሚያስተምሯቸው፤ ስልጣን ላይ እየቆዩ በሄዱ ቁጥር የኢትዮጵያ ህዝብ እራሱን ነጻ ለማውጣት የተወሳሰበ ችግር ሊገጥመው ይችላል።

 

በሀያ ሁለት አመታት ጉዞአችን እያየነው ያለ ነገር ወያኔ የነደፈው እቅድ ያለ አንዳች ሳንካ እየተሳካ እየተሳካ በመሄድ ላይ ሲገኝ የኛ የተገዢዎቹ ኢትዮጵያውያን እቅድ ጩኸት ብቻ ሆኖ እሱም ሰሚ የሌለው የምድረበዳ ጩኸት እየሆነ መምጣቱን ነው። መላውን የሀገሪቱ ጦር ሰራዊት  በራሱ የአማጽያን ቡድን ለውጦ፤ ወያኔ ፖለቲካውንም ኢኮኖሚውንም መቶ በመቶ በበላይነት ተቆጣጥሮ፤ በፈለገው አይነትና ሁኔታ ህዝቡን በዘር አጥሮ፤ ከፋፍሎ፤ ተቆጣጥሮ፤ የኢትዮጵያን ህዝብ መተሳሰሪያ ያንድነቱን እትብት በጣጥሶ እየጨረሰ ነው። ህዝቡ አንድ ቋንቋ እንዳይናገር የአማርኛን  ብሄራዊ ቋንቋነት ሰርዞ፤ የህዝቡን ህጋዊና ታሪካዊ የባለቤትነት መብት በሀይል አግዶ የባህር በር እንዳይኖር አሰብን ለጠላት ሰቶ፤ ምእራቡን የኢትዮጵያ ክፍል አንድሺህ ስድስት መቶ ኪሎ ሜትር ርዝመት ከሰላሳ እስክ ስልሳ ኪሎሜትር ስፋት ለሱዳን ሰቶ፤  መላውን ህዝብ ከየቀየው እያፈናቀለ፤ እያሳደደ፤ እየገደለ፤ ወህኒ እያጎረ የሀገሪቱን ለም የርሻ መሬት ለባእዳን በርካሽ እየቸበቸበ፤ ገንዘቡን እንደፈለገው እያደረገ መኖሩን ቀጥሏል። መላውን የሀገሪቱን ሀብት በህውሀት ቡድን መዳፍ ውስጥ አስገብቶ፤ የኢትዮጵያና የኢትዮጵያዊነት መለያ የሆኑ ባህላዊ፤ ታሪካዊ፤ ሀይማኖታዊ ውርስና ቅርሶችን ሁሉ አውድሞ፤  ገዳማትን አፍርሶ፤ ሀውልቶችን ነቅሎ፤ ታሪካዊና መታሰቢያ ስሞችን ሁሉ ለውጦ፤ ሀይማኖታትን አርክሶ ክልሶ፤ ከፋፍሎ  በጣብጦ፤ አበጣብጦ፤ የነበረውን ሊያጠፋ ያልነበረውን ሀይማኖት ከየትም ፈልጎ እያመጣ፤ ህዝብ ላይ እያጣበቀ እየጫነ፤ ሌላም ሌላ ….የጥፋት ጎዞውን ያለ እንቅፋት ቀጥሏል።

እርግጥ ነው ፤ የኢትዮጵያ ህዝብ ለወያኔ እጅግ የሚያስፈራውና የሚያሳስበው የማይናወጥ አንድ አቋም እንዳለው በተደጋጋሚ አጋጣሚውን ሲያገኝ አሳይቷል። ወያኔ እንደማናቸውም ቅኝ ገዢዎች ሁሉ ማናቸውንም ዋጋ ከፍሎ እየሰራበት ያለው ከፋፍሎ የመግዛት ዘይቤ፤ ይህ ቡድን በገመተው ልክ የኢትዮጵያን ህዝብ አልከፋፈለለትም። ከስምንት አመት አገዳ በሁዋላ በቅርቡ ለሙከራ የተጀመሩት ሰላማዊ ሰልፎች፤ ያዲስ አበባውም የወሎውም የጎንደሩም ሁሉም ያረጋገጠው ነገር ቢኖር የኢትዮጵያ ህዝብ ከሀያ ሁለት አመታት በፊት የነበረ አብሮነቱን፤ እንድነቱን ምንጊዜም ከልቡ እንደማያወጣው ነው።

አዎ  የኢትዮጵያ ህዝብ ለየብቻው እንዲሆን፤ ለየብቻው እንዲያስብ፤ ለየብቻው  እንዲናገር፤ በሀይል ተከልሎ ታጥሯል። ከስድስት መቶ አመታት በላይ የጋራ መግባቢያ የነበረውን የአማርኛ ቋንቋ ሁሉም ክልል እናዳይናገር ተከልክሏል። ህጻናት የራሳቸውን ቋንቋ ብቻ እየተናገሩ እንዲያድጉና እንዲማሩ ከሌላው ኢትዮጵያዊ ጋር የሚያገናኛቸው ሌላ ቋንቋ እንዳይማሩ ተደርገዋል። የወያኔ ትልሙ ከኢትዮጵያ ህዝብ በብዛቱ ከፍተኛውን ድርሻ የሚይዘውን ወጣት በሀምሳ አመት ውስጥ እንደጋሪ ፈረስ አንድ አቅጣጫ ብቻ የሚያይ አድርጎ ከፈጠረው፤ የሚያስተሳስረው ቋንቋ፤ ባህል፤ ታሪክ፤ የጋራ ሀገር ካሳጣው በቀላሉ ይበተናል፤ ኢትዮጵያ የምትባል ሀገር አትኖርም ነው። ኢትዮጵያ ግን በኢትዮጵያ ህዝብ ልብ ውስጥ አንድነቷን ጠብቃ ለዘለአለም ትኖራለች። በወያኔ ፋሺሽቶች ከርሰ መቃብር ላይም በልጆቿ አንድነት አንዲት ሀያል ኢትዮጵያ ዳግም ትነሳለች።

ወያኔ የያዘውን ስልጣን ተቆጣጥሮ እስከመጨረሻው ለመዝለቅ የሚያስችለው እርግጠኛ የሆነበት ሌላው በተግባር ያዋለው ዘዴ፤ ጦር ሀይሉን ደህንነቱና ፖሊሱን በራሱ ሰዎች ማስይዙ እንዳለ ሆኖ፤ የህውሀት የጦር አለቆች ቀጥተኛ የሀገሪቱ ሀብት ባለድርሻ መሆናቸው ነው። በዛሬዋ  ዓለም ምንም አይነት የተለየ ሞያ ሳይኖረው፤ በሚሊዮን የሚቆጠር ገንዘብ እያወጣ ለግሉ ህንጻ መገንባት የቻለ፤ በሚሊዮኖች የሚቆጠር ገንዘብ በኢንቨስትመንት የሚያንቀሳቅ ጀነራል፤ ኮሎኔል፤ ሻለቃ ወዘተ….የሚባል፤ ስራ ላይ ያለ ወታደር ያላት ሀገር ኢትዮጵያ ብቻ ነች። እነዚህ ባለሀብት መኮንኖች የኛ ነው የሚሉት መንግስት እንኳ ለለውጥ ቢነሳና ያ ለውጥ ይህን ያለ አግባብ  በጃቸው ያከማቹትን ሀብት ያሳጣናል ብለው ከሰጉ ፤ የወያኔ ጀነራሎች ከላይ ያለውን የወያኔ አካል በሀይል አስወግድው ራሳቸው ስልጣኑን እንደሚይዙት ልንጠራጠር አይገባም። ስለዚህ ሁሉም የህውሀት አመራር በየፈርጁ ለራሱ ህልውና ሲል በስነስርአት የሀገሪቱን ሀብት እየዘረፈና እየተከፋፈለ በመኖር ላይ ይገኛል። ህዝብ ለለውጥ ልነሳ ካለ እስካሁን እያደረገ እንዳለው ማናቸውንም ወታደራዊና አስተዳደራዊ እርምጃ እየወሰደ ይቀጥላል። እነዚህን በሀገር ሀብት ዘረፋ የደለቡ ደናቁርት የወያኔ ነፍሰገዳይ የጦር አለቆች፤ ከታች ያለው የሰፊው ህዝብ ልጅ የሆነው መለዮ ለባሽ ካላመጸና እግር ተወርች እያሰረ ለፍርድ ካላቀረባቸው፤ ግደል ባሉት ቁጥር የራሱን ቤተሰብ እየገደለ፤ የወገኖቹን ደም እያፈሰሰ እነሱ እየበለጸጉ መኖር እንዲቀጥሉ፤ ስርአቱም በጥቂት የአንድ ጎሳ አባላት የበላይነት ተገንብቶ እንዲቀጥል ከፈቀደላቸው ይህች ሀገርና ይህ ህዝብ ፍዳቸው ይቀጥላል።

የጦር አዛዦቹ የሀብት ምንጭ ማእከላዊ መንግስቱ ብቻ አይደለም። የየክልል አሻንጉሊቶቻቸው ከፍተኛውን ድርሻ ይይዛሉ። አሰራሩ እንዲህ ነው። በአራቱም የሀገሪቱ ማእዘናት የጦር እዝ ማእክሎች ይገኛሉ ። የዚያን አካባቢ እዝ የሚያዙት የህውሀት ጀነራሎች ስራቸው፤ ጦሩን ማንቀሳቀስና መምራት ማዘዝ ብቻ አይደለም። ባካባቢያቸው ያሉ ክልሎችን ለምልክት ካስቀመጧቸው የክልል ፕሬዚደንቶች ጀርባ ሁነው፤ ክልሉን ያስተዳድራሉ። ይመራሉ። ሹማምንቱን ይቆጣጠራሉ። ያዛሉ። ከማእከላዊ መንግስት የሚለቀቀውን በጀት ያውቃሉ፤ ይቆጣጠራሉ።

ምሳሌ…. ሀረር ከተማ መቀመጫውን ያደረገው የምስራቅ እዝ አዛዥ ጀነራል፤ የሀረሪ ክልላዊ መንግስትና የሱማሌ ክልላዊ መንግስት  ባለስልጣናትን ያዛል፤ ይቆጣጠራል።  በየአመቱ የክልሎች በጀት እንደተለቀቀ የህውሀት ኩባንያዎች በያቅጣጫው አብረው ይለቀቃሉ። በየክልሉ በበጀት አመቱ ይሰራሉ የተባሉትን አንዳንድ ነገሮች ተሻምተው ይከፋፈላሉ። ከባጀቱ የተወሰነውን ይወስዳሉ። ከዚያ የተወሰነ መጠን የክልልሉ ሹማምንት እንዲበሉ ይደረጋል። ይህም የሚደረገው በኮረብሽን እንዲነካኩና የሚታዘዙትን አንፈጽም ካሉ በቀላሉ እስር ቤት ተወርውረው ሌላ ማስቀመጥ እንዲቻል ነው። ይህን ሁሉ በንቃት ይሚያስፈጽመው የወያኔ ጀነራል፡ ኮሎኔል፡ ወይም ሻለቃም ሊሆን ይችላል። በክልሉ ለምልክት የሚሆኑ ጥቂት ስራዎች እንዲሰሩ ያ የወያኔ አዛዥ ከተከታተለ በኋላ የተጋነኑና የውሸት ሪፖርቶች እንዲዘጋጁ ይደረጋል። የዚያ ክልል ፕሬዚዳንት የተረፈውን ገንዘብ ይዞ ወደ ጀነራሉ  ቢሮ እንዲመጣ ይታዘዛል።  ያንን ገንዘብ የተረከበው ጀነራል የሚበቃውንና የሚፈልገውን ያህል ወደ ግል ባንኩ ካስገባ በኋላ፤ ለሌሎቹ ማካፈል ካለበትም የሚያደርገውን ራሱ ይወስናል።

ለዚህም ነው ኢትዮጵያን የወረሯት አዛዥ የትግራይ ታጋዮች  በሙሉ በኢንቨስትመንትና በግንባታ ላይ የተሰማሩት፡፡ ለዚህም ነው እስከመጨረሻው እየገደሉ ጥቅማቸውን ያስጠብቃሉ እንጂ ሰላማዊ ትግል  በሚል ጨዋታ እጃቸው የገባውን ስልጣን አሳልፈው የማይሰጡት።

ምንድነው መደረግ ያለበት?

ይህን በኢትዮጵያ ህዝብ ልብ ውስጥ ተዳፍኖ ያለውን የአንድነትና የትግል ስሜት ጎልቶ እንዲወጣ ማድረግ ከንግዲህ በኋላ ጊዜ የሚሰጠው ጉዳይ አይደለም። አብረው ሲጋፈጡት ሞትም አይከብድም። አንዱ አደባባይ ወቶ የተቃውሞ ጩኸቱን ሲያስማ ሌላው በፍርሀት ቤቱ ተሸሽጎ አጨንቁሮ በመስኮትና  በበሩ ቀዳዳ የሚያይበት ሁኔታ ዛሬ ላይ መቆም አለበት።

ከዚህ መንግስት ጋር በሙሉ ልብ ለስርአቱ እድሜ መራዘም እየሰራችሁ ያላቸሁ ምሁራን፤ በኢትዮጵያ ህዝብና በሀገሪቱ ላይ እየደረሰ ያለው አፈና፤ ሰብአዊ መብት ረገጣና ግፍ፤ ትክክል አለመሆኑ ሳይገባችሁ ቀርቶ ሳይሆን ህሊናን ለጥቅም አሳልፎ የመሸጥ ጉዳይ ነው ችግራችሁ። ግልጽ ነው። እርግጥ ተፈጥሮን ተመክሮ ላያድነው ይችላል። አንድ ሰው በተፈጥሮው ራስ ወዳድ፤ ውሸታም፤ ሌባ፤ መስሎ አዳሪ፤ ጥቅም እንጂ ሰብአዊ ርህራሄ የማያውቅ ከሆነ፤ ለራሱ የሚጠቅመውን ነገር ካተረፈ፤ ህዝብ ያስፈጃል፤ ግፍም ይፈጽማል። ስለዚህ እናንት ከወያኔ ጋር የተለጠፋችሁ ቅጥረኛ ምሁራን፤ አማራ፤ ኦሮሞ፤ ደቡብ ወዘተ….ወያኔ ባላሰባችሁት ሁኔታ እያንዳንዳችሁን በልቶ እንደሚጨርሳችሁ ከወዲሁ ተገንዝባችሁ፤ የተጠቀማችሁትን ተጠቅማችኋል፤ የያዛችሁትን ይዛችሁ እራሳችሁን ከወያኔ መንግስት አግልሉ። የነጻነቱን ትግል ተቀላቀሉ። የበደላችሁትን ህዝብ ካሱ።

ሌሎቻችሁ በተቃዋሚውም ወገን በደጋፊውም ወገን ሳትሆኑ፤ መሀል ላይ ተደላድላችሁ፤ ድምጣችሁን አጥፍታችሁ፤ አድፍጣችሁ፤ በቀጥታ እናንተ ላይ ስላልደረስ ብቻ በሀገር በወገን ላይ የሚደርሰውን ግፍ እንዳላየ እንዳልሰማ ሁናችሁ፤ በራሳችሁ ህይወትና ምቾት ዙሪያ  እየተሽከረከራችሁ ይህችን ቀውጢ ቀን ለማሳለፍ የምትፈልጉ ኢትዮጵያውያን ይህ መሀል ሰፋሪነት ያስገኘላችሁ ሰላም ነገ ጠዋት ይደፈርሳል። ህዝብን እየጨፈጨፍኩ መግዛቴን እቀጥላለሁ ብሎ የቆረጠ ነፍሰ ገዳይ መንግስት ባለበት ሀገር ውስጥ የናንተ ሰላም አይዘልቅም። በህዝባዊ ትግል የቆሰለ መንግስት እንዳበደ ውሻ ባጠገቡ ያየውን ሁሉ ነው የሚቦጭቀው። አካሉንም ሳይቀር ስለዚህ…. ስለዚህ ከመሀል ውጡና ህዝቡ እንደሚሆነው ሁኑ። የህዝቡን የተቃውሞ ድምጽ አበራክቱ።

በተራ ወታደርነትና የበታች መኮንንነት ደረጃ ያላችሁ የመከላከያ ሰራዊት አባላት፤ ይህ እንደከብት እየነዳ የሚያዛችሁ የወያኔ ታጋይ አዛዥ ከናንተ የበለጠ አዋቂ፤ ከናንተ የበለጠ ጀግና አይደለም። ቀን ያነሳው የመሀይም ሽፍታ ጥርቅም ነው። የአንድ መንደር ምልምል ነው። እናንተ ግን የመላው ኢትዮጵያ ህዝብ ልጆች ናችሁ። የኢትዮጵያ ህዝብ ቤተሰባችሁን የኑሮ ውድነት እየጠበሰው፤ የወያኔ አመራሮችና ታጋይ ጀነራሎች እንዲሁም ቅጥረኞቻቸው በሚሊዮን ዶላር ንግድ ተሰማርተው የአለም ሀብታም ሰዎች እንደሚኖሩት ይኖራሉ። በናንተ ደምም ይነግዳሉ። ለምሆኑ እናንተ ለሰላም ማስከበር ተልኮ ሩዋንዳ፤ ሶማሌ፤ ሱዳን፤ እየሄዳችሁ ስትሞቱ የተባበሩት መንግስታት ለያንዳንዱ ወታደር የሚከፍለውን ወፍራም አበል ተቀብላችሁ ወደ ቤተሰብ ልካችሁ ታውቃላችሁ? ስንቶቻችሁስ ናችሁ የተባበሩት መንግስታት ለናንተ አበል እንደሚከፍል የምታውቁ? የወያኔ ታጋይ አዛዦች ተቀብለው ወዴት እንደሚያደርሱትስ የምታውቁት ነገር አለ?

አንድ ወታደር በህዝብ ላይ አደጋ እንዲያደርስ ቢታዘዝ ያለቃውን ትዛዝ አልቀበልም የማለት የሞራልና የህግ መሰረት እንዳለው ይታወቃል። ወያኔ የኢትዮጵያን ህዝብ ከአብራኩ በወጡ ልጆቹ እያስገደለ፤ እስከመቼ ድረስ ነው ረግጦ የሚገዛውና የሀገሪቱን ሀብት የሚያጋብሰው? ወጣቱ የኢትዮጵያ ጦር ሰራዊት እንደ ግብጽ፤ እንደቱኒዚያ ሰራዊት ከሀገርና ከህዝብ ጎን መቆም ይጠበቅበታል። የአንባ ገነኖች ደህንነት ሳይሆን የሀገርና የህዝብ ደህንነት ነው የሀገር ፍቅር ላለው ሰራዊት ቅድሚያ የሚኖረው። ሀይል በጁ ነው። የህውሀትን ታጋይ አዛዦች ሰብስቦ ወደ እስር ቤት ማጎርና ስልጣኑ ላይ ያሉትን አሽመድምዶ፤ ለህዝቡ የምርጫ ነጻነት መስጠት ያስፈልጋል። ህዝቡ በቶሎ ጊዚያዊ የሽግግር መንግስት አቋቁሞ፤ ለመደበኛ ምርጫ ሰላማዊ ስራ እንዲሰራ ማድረግና ከውስጥም ከውጭም ለሚነሱ የሀገር ጠላቶች ምላሽ ለመስጠት መሰማራት ያስፈልጋል።

ተቃዋሚ ነን የምትሉ ድርጅቶም አንዱ ያንዱን ጥረትና ትግል እያንኳሰሰ፤ ራሱን እያወደሰ ፤ እርስ በርስ መናቆር ከቀጠለ አተካራችሁ የኢትዮጵያን ህዝብ ጥርጣሬና ውዥንብር ውስጥ ስለሚከተው አንዳችሁንም አያምን። አንዳችሁንም አይከተል። መጀመሪያ ለራሳችሁ ተከባበሩ። ተባበሩ። አንዲት ጎጆ ለመገንባት አብረው የተሰማሩ ሰዎች ሳር አይሻማሙም ይባላል። የሁላችሁም አላማና ግብ ወያኔን አስወግዶ አንዲት ዲሞክራሲያዊት ኢትዮጵያን ለመገንባት እስከሆነ ድረስ፤ የተለማችሁት ዘዴና አካሄድ መለያየቱ የሚጠበቅና መሆንም፤ መኖርም ያለበት አማራጭ ነው እንጂ፤ አንዳችሁን ካንዳችሁ የሚያባላ የማይታረቅ ልዩነት አይደለም። በማይረባ ጥቃቅን ልዩነት በህዝብ ፊት ስትናቆሩ፤ ህዝቡ ሁላችሁንም አንቅሮ ተፍቶ፤ ከራሱ ውስጥ የሚያታግሉትን ሰዎች አውጥቶ ትግሉን ይቀጥላል። ያከመሆኑ በፊት ግን ተከባብራችሁ፤ ተባብራችሁ ህዝቡን በማስተባበር የለውጥ እንቅስቃሴውን አፋጥኑ።

የኢትዮጵያ ወጣቶች ወያኔ ሀገር እያሳጣችሁ፤ ተስፋ እያሳጣችሁ በመጓዝ ላይ መኖሩን ሳትዘነጉ፤ ራሳችሁንና ሀገራችሁን ህዝባችሁን ለማዳን ተነሱ።

በጫትና በሀሺሽ፤ በአልኮል ናላችሁን የምታዞሩ፤ ገሚሶቻችሁም የሀገር ፍቅርን ስሜትና የትግልን ስሜት በሚያኮላሹ ሀይማኖቶች ተተብትባችሁ፤ በእውን ለምትኖሩበት የምድር ፈተና መፍትሄ እንደመፈለግ ከሞት በኋላ ስለምታገኙት ህይወትና ሞቾት ስትቃዡ፤ ጌታ ጌታ እያላችሁ በየ አጥቢያው ስታላዝኑ ወያኔ ምድሪቱን በላያችሁ ላይ እየሸጣት ነው። ከጴንጤውም ከጆቫውም ከሌላውም የቅዥት አለም ውስጥ ውጡና እናት ሀገራችሁ ኢትዮጵያን ከአርባ ጊዜ በላይ የሚጠራት መጽሀፍ ቅዱሳችንን ይዛችሁ፤ ለትግል የቆረጡ ወጣቶችን ተቀላቀሉ።

ኢትዮጵያ ዳግም ትነሳለች!

ሞት ለወያኔ!

lkebede10@gmail.com

 

↧
↧

ኢሳት ያኣማራ ቊጥር የቀነሰበትን ምክንያት አጋለጠ:

$
0
0

ያኣማራ ሴቶች ክትባት ከተከተቡ በሃላ መውለድ እንዳቃታቸው ለኢሳት ተናገሩ:

 

↧

ጥሩነሽ ዲባባ –ጠይሟ ልዕልት

$
0
0

tirunesh dibaba
ጠይሟ ልዕልት
የሩጫው ድማሚት
ሰዓት ጠብቃ ስትፈነዳ
አንድም ታምራለች እንደ ጽጌሬዳ
አንድም ታርዳለች እንደ ካባው ናዳ ፡፡
ጠይሟ ቀስተ ዳመና
ባለብዙ ልዕልና
የስንቱን አይን በረገደች ?
በወቸው ጉድ በለጠጠች ::
የስንቱን ልብ አሞቀች ?
በፍቅር መዳፍ ጣለች ::
እናትስ ትውለድ ያንቺን አይነቱን አቦሸማኔ
ህዝብ የሚወድ አስተኔ ፡፡

ከአለማየሁ ገበየሁ

↧

ሙስሊም ወገኖቻችንን የሚያዋከወበውንና የሚያሸብረውን የወያኔ/ኢህአዴግ ተግባር እናውግዝ፣

$
0
0

 meson h

ከሙስሊም ወገኖቻችን ጎን እንቁም። እናውግዝ፣ ከሙስሊም ወገኖቻችን ጎን እንቁም።

የእስልምና ሃይማኖት ተከታዮች፣ በየትኛውም አለም ክፍል፣ የኢድ አል ፈጢር በአል በደስታ አክብረው ሲውሉ፤  የኢትዮጵያ ሙስሊሞች ብቻ በአገራቸው መንግስት ተብዬ ሲዋከቡና ሲሸበሩ ውለዋል። በብዙ የኢትዮጵያ ከተሞች፣
በተለይ ባዲስ አበባ፣ የኢድ አል ፈጢር በአሉን ለማከበር የተሰበሰበውን ሕዝበ-ሙስሊም፣ ፖሊስ በዱላና በጠመንጃ  ባካሄደው ሺብር፣ ህፃንና ነፍሰጡር ጨምሮ ህይወት ማለፉ፣ ብዙ ሰው መቁሰሉና ቁጥሩ ከግምት በላይ የሆነ ሕዝብ  መታሰሩ በሰፊው ተነግሯል።
ይህ በኢድ አል ፈጢር ክብረ-በአል ወቅት የተካሄደው ሺብር፤ ወያኔ/ኢህአዴግ ከአንደ አመት ተኩል በላይ የቀጠለውን፣  ”ድምፃችን ይሰማ፣ መብታችን ይከበር”oበማለት ሙስሊሙ ህብረተሰብ የሚያካሂደውን ሰላማዊ ትግል ለማፈን በተለያዩ  ወቅቶችና በተለያዩ ቦታዎች ሲያካሂደው የኖረው ሺብር አነዱ አካል ነው። ከኢድ አል ፈጢር ክብረ-በአል ሁለት ቀን  ቀድሞ፣ በኮፈሌ ወረዳ (አርሲ) የተካሄደው ጪፍጨፋ የቅርብ ምሳሌ ነው።
ወያኔ/ኢህአዴግ የኢትዮጵያን ሕዝብ በቁጥጥሩ ዉስጥ አስገብቶ እንደፈለገው ሲያመሳቅል ከ20አመት በላይ ያለምንም  ተጋፊ ሃይል ቢቆይም፤ ለቀጣዩ እድሜው ተፃራሪ ሃይል እንዳይነሳበት፣ ለማንኛውም ድርጅት፣ የፖለቲካ፣ የማህበራዊ፣  የሙያ፣ የሃይማኖት ወዘተ፣ ”ምስል-ጥጃ”oበማበጀት ሃቀኛ ድርጅቶችን ሲያኮላሺ ኖሯል። እስካሁን ድረስ ቀጣይና  ጠንካራ ተቃዉሞ ያጋጠመው ከሙስሊም ኢይዮጵያዊያን ብቻ በመሆኑ፣ በህዝበ-ሙስሊሙ ላይ እዬከፋ የመጣ ሺብር  ቀጥሏል።
በዚህ የሺብር ዘመን፣ ሆዳቸውን ወድደው ነፍስ የማትፋት ትዛዝ የሚፈጽሙትንና በተሰጣቸው ስልጣን በመመካት  ህዝብ የሚያሸብሩ ግለሰቦችን በወቅቱ ፍርድ ላይ ማቅረብ አይቻልም። ዘመኑ ”አባቱ ዳኛ ልጁ ቀማኛ”oእንደሚባለው
ነውና። ነፍስ አስገዳዩ የወያኔ/ኢህአዴግ ሥርዓት፣ ፍርድ ሰጪም የወያኔ/ኢህአዴግ ሥርዓት በመሆኑ ነፍሰ-ገዳዮች በነፃ  ይኖራሉ። ይሁንና የአገራቸው ጉዳይ የሚያስጨንቃቸው ዴሞክራሲያዊ ሃይሎች ሁሉ በነፍስ ግዳይ መጠየቅ ያለባቸውን  ግለሰቦች፤ ቀን የወጣ እለት ለፍርድ የሚቀርቡበትን ሁኔታ ማመቻቸት ይኖርባቸዎል።
የህዝበ-ሙስሊሙ ’’ድምፃጭን ይሰማ፣ መብታችን ይከበር”oጥያቄ ህዝባዊ ጥያቄ እንደ መሆኑ መጠን የሁላችንም ጥያቄ  ነው። ስለሆነም የወያኔኢህአዴግን የሺብር ተግባር ከማውገዝ ባሻገር ከሙስሊም ወገኖቻችን ጎን መሰለፍ ግዴታችን
መሆን አለበት።
ህዝባዊ ትግል ይፋፋም፣
ዴሞክራሲ ይስፋፋ፣ አንድነት ይጠንክር፣
ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር።
መኢሶን
ነሃሴ 3 ቀን 2005 ዓ ም

 

↧

‹‹ኢትዮጵያውያን በፖለቲካ ጉዳዮች አማራጭ ዕድሎችን ሊያገኙ ይገባል›› –ተሰናባቹ የአሜሪካ አምባሳደር ዶናልድ ቡዝ

$
0
0

AmbaUSA11 AUGUST 2013 ተጻፈ በ ዮሐንስ አንበርብር
‹‹ኢትዮጵያውያን በፖለቲካ ጉዳዮች አማራጭ ዕድሎችን ሊያገኙ ይገባል››
ተሰናባቹ የአሜሪካ አምባሳደር ዶናልድ ቡዝ
በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር በመሆን ላለፉት ሦስት ዓመታት በአዲስ አበባ ቆይታ ያደረጉት አምባሳደር
ዶናልድ ቡዝ የኢትዮጵያ ተልዕኳቸውን ሰሞኑን አብቅተዋል፡

Download (PDF, 270KB)


↧
↧

በጥሩየ ዳግም ኮራን !ከ ነብዩ ሲራክ

↧

የታሰሩት የአንድነት አመራሮችና አባላት ፖሊስና ደህንነት ባዘጋጁት ሰነድ ላይ እንዲፈርሙ እየተገደዱ ነው

$
0
0
ኢቲቪ ባልተጠራብ አንድነት በመብራት ሃይል እያካሄደ ባለው ስብሰባ ላይ መጥቶ የደገናቸው ካሜራዎች፡፡

ኢቲቪ ባልተጠራብ አንድነት በመብራት ሃይል እያካሄደ ባለው ስብሰባ ላይ መጥቶ የደገናቸው ካሜራዎች፡፡

በአዲስ ጎማ አካባቢ አቃቂ ቃሊቲ ፖሊስ መምሪያ የታሰሩት የአንድነት ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮችና አባላት ደህንነቶችና ፖሊሶች ባዘጋጁት የክስቻርጅ ላይ በግዳጅ እንዲፈርሙ ጫናዎች ቢደረጉባቸውም አንፈርምም በሚለው አቋማቸው ፀንተዋል፡፡ ደህንነቶቹና ፖሊሶቹ ያዘጋጁት የክስ ቻርጅ ፡- 1ኛ. “አንድነት ፓርቲን በጥቂቱ ይተዋወቁ” በሚል ርዕስ በተዘጋጀው ብሮሸር ላይ “ኢህአዴግ መራሹ መንግስት በመሳሪያ አፈሙዝ ታግዞ በይስሙላ ምርጫዎች ተመረጥኩ በማለት ሀገራችንን ከጀመረ 22 ዓመታት ተቆጠሩ፡፡” በማለት የቀረበው በቂ ማስረጃ የለውም፡፡ 2ኛ. “የሚሊዮኖች ድምፅ ለነፃነት በኢትዮጵያዊ አንድነት ወደ ተስፋ ጉዞ” በሚል ርዕስ የተዘጋጀው በራሪ ወረቀት ላይኢህአደድግ በየጊዜው በሚያወጣቸው ህዝብን ማፈኛ አዋጆች የታሰሩ ጋዜጠኞች፣የፖለቲካ ፓርቲ መሪዎችና የእምነት ነፃነት እንዲከበር የታገሉ የሙስሊሙ ህብረተሰብ መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ አባላት በአስቸኳይ ፣ የፀረ ሽብር ህጉ ህገ-መንግስቱን በግልፅ የሚንድ ስለሆነ እንሰረዝ የሚለው ግልፅ ስላልሆነ እንዲሰረዝ” የሚለው ግልፅነት ይጎድለዋል፡፡ በሀይማኖት ውስጥ ጣልቃ ገብቶ ማበጣበጥ ነው፡፡ 3ኛ. ወደ ፖሊስ ጣቢያ ሂዱ ስትባሉ ፍቃደኛ ባለመሆን ሁከት ፈጥራችኋል፡፡ የሚሉ ክሶችን የያዘ ነው፡፡ ‪#‎Millionsofvoicesforfreedom‬ ‪#‎Ethiopia‬ ‪#‎UDJ‬ ‪#‎ADDISABABA‬ -

↧

የሥላሴዎች እርግማን (ሁለት)፤ አደህይቶ ማድከም (መስፍን ወልደ ማርያም)

$
0
0

መስፍን ወልደ ማርያም

ሐምሌ 2005

ከታትፎና ለያይቶ በማዳከም ቤቱን አፍርሶና መሬቱን ነጥቆ፣ ከሥራው አፈናቅሎና ሥራ አሳጥቶ ያለርኅራኄ ማደህየት በፕሮግራም የተያዘና በውጭ ኃይሎች የሚደገፍ ሥራ ነው፡፡

Pro Mesfinለጥቂት ዓመታት በአሜሪካ ቆይቶ የመጣ አንድ ጓደኛዬ ራሱን በሁለት እጆቹ ይዞ ‹‹አዲስ አበባ በመሬት መናወጥ ፈራርሳ በመጠገን ላይ ያለች ከተማ ትመስል የለም እንዴ!›› አለኝ፤የመሬት አይደለም አንጂ የመናወጥ ነገር በእርግጥ አለ፤ የመሬት መናወጥ ባይደርስባትም የአእምሮ መናወጥ የመታት ከተማ ነች አልሁት፤ ቅንጅት ነፍሱን ይማረውና በፖሊቲካው መድረክ ብልጭ ብሎ ድርግም ካለበት ዓመት ጀምሮ በአዲስ አበባ ታይቶ የማይታወቅ የማፍረስና የመገንባት ሥራ በአንድ ላይ ጎን ለጎን ሲካሄድ እያየን ነው፤ ከጥንስሱ ጀምሮ የማሰብ ችግር ውላጅ መሆኑ በግልጽ ይታያል፤ ብዙ አገሮች አዳዲስ ከተማዎችን ሠርተዋል፤ ጥቂቶቹን ለመጥቀስ ሕንድ፣ ናይጂርያ፣ ብራዚል አሉበት፤ የወያኔ/ኢሕአዴግ ግን የተለየ ነው፤ አዲስ ከተማ እየሠራ ሳይሆን የጥንቱን እያፈረሰ ነው፤ ደርግ ሲጀምር ከጥንቱ ሥርዓት ጋር በመጣላት ነበር፤ ወያኔ ሲጀምር ግን ከማን ወይም ከምን ጋር ተጣልቶ አንደሆነ በግልጽ ባይታይም በጥላቻ መወራጨቱ ይታይ ነበር፤ ጎልቶ የወጣውም የችግረኛ ጉጉትና ምኞት፣ ሽሚያና ዝርፊያ የወያኔ ዓላማ ከራሱ የማያልፍ መሆኑን ያመለክት ነበር፤ በውጤቱም የሆነለት ያባትህ ቤት ሲዘረፍ እንደሚባለው ሆኖ ከውጭ ባንክ ተርፎ፣ ከአገር ውስጥ ባንክ ተርፎ፣ በጆንያና በጉድጓድ በሚልዮን የሚቆጠር ገንዘብ ያስቀመጠ ተደላድሎ እየሳቀ ይዝናናል፤ ያልሆነለትም በየሜዳው ያለቅሳል፤ ከተማው በሙሉ በማፍረስና በመገንባት ይታመሳል፤ ይተራመሳል፤ ዋናው ዓላማ ሕዝቡን ማዳከም ነው፤አዳክሞም ማደህየት ነው፡፡–

  • ይህ ሁሉ መንገድ የደሀውን ቤት ሁሉ እየመነጠረ ሲረዝምና ሲሰፋ፣
  • የደሀ ቤቶች ተመንጥረው መንገዱ ከረዘመና ከሰፋ በኋላ ባለሥልጣኖች በድንገት ስለባቡር የሚያስታውሳቸው አማካሪ ሲያገኙ፤
  • የድሆች ቤቶች እየተመነጠሩ የሰፋውን መንገድ እያፈረሱ ሲያጠቡት!
  • ቤቶች ሲፈርሱና መንገዶች ሲረዝሙ፣ መንገዶች ሲሰፉና ሲጠቡ፣
  • መንገዱ ለባቡሮች ሲቆፈርና ሲተራመስ፣
  • መንገዱ በደሀዎቹ ቤቶች ፍርስራሽ ተጨናንቆ በደሀ እንባ ሲጨቀይ፣
  • ለደሀዎች መኖሪያ ኮንዶሚንየም እየተባለ በሚልዮን የሚቆጠር ገንዘብ ሲገባና ሲወጣ፣
  • የመንገዱና የባቡሩ ወጪ ከኮንዶሚኒየሙ ሼል ጋር ተዳብሎ በቢልዮን የሚቆጠር ብር እየተተራመሰ ከመንግሥት ኪስ ሲፈስ፣
  • ‹‹የመንግሥት ሌቦች›› የሚፈስሰውን እየለቀሙና እየተወዳደሩ ‹‹በምድር ላይ ሳንበተን ስማችንን እናስጠራ›› ብለው ግንበ-ሰናኦርን ሲክቡ፣
  • የሙስና ተከላካዮች ፈራ-ተባ እያሉ በእርሳስ ሲመዘግቡና ግንዱንና ስሩን ሳይነኩ በኢዮባዊ ትእግስትና በሰሎሞናዊ ፍርድ ቅጠሎቹን እየከረከሙ ሲያረግፉ፣
  • ሙስና ሾሊ እየጠነከረ ግንዱም እንደግንበ-ሰናኦር ወደሰማይ እያደገ ሲሄድና ቅጠሉም ወዲያው ሲለመልም፤
  • ደሀነትም በጌትነት እየተጋጠ በሞትና በሕይወት መሀከል ሆኖ እያቃሰተ ሲያድግ፣
  • ለደሀነት መቀነሻ የሚባለው ሁሉ ደሀነትን ለማባባስ ሲውል፣

የደላው ይደሰታል፤ የተጎዳው እንባውን በየመንገዱና በየቤተክርስቲያኑ፣ በየቤተ መስጊዱ ይረጫል፤ የሚታዘብ ያንጎራጉራል፤

…

በቁንጣን፣ በስካር ጥቂቶች ሲንሩ፣

ብዙዎቹ ደግሞ በረሀብ መንምነው በቁንጫ ሲያርሩ፣

የደሀ እንባ ሲጎርፍ መሬቱ ሲሸበር፣

ዝብርቅርቁ ወጣ፤ ሕይወት ትርጉም አጣ፤

…

መንገዱ ጠበበ፤ ትርምስምሱ በዛ፤

እሪታው፣ ኡኡታው ቀለጠ እንደዋዛ፤

መሬቱም፣ ዓየሩም በክፋት ጠነዛ፤

ጥላቻና ቂሙ በሰፊው ተነዛ፤

እምቢልታው ሲጣራ ነጋሪት ሲያገሳ፣

የአለው ሁሉ ሞቶ የሞተው ሲነሣ፣

ምጽዓት መድረሱ ነው፤ ሊስተካከል ነው ፍርድ፤

በግና ፍየሉ ሊለዩ በገሀድ!

 

አፍርሶ መገንባት ዘለቄታ ያለው እድገትና መሻሻል ያስከትላል ብለው የሚያምኑ ከኋላቸውም ከፊታቸውም የሚያዩት ሁሉ ያከሸፋቸውና የከሸፉ ናቸው፤ ወደኋላ እንዳያዩ ታሪክ የላቸውም፤ ወደፊት እንዳያዩ ራእይ የላቸውም፤ የሥላሴዎች እርግማን!

↧

አንድነት ፓርቲ ነሃሴ 5 ቀን 2005 ዓ.ም በመብራት ሃይል አዳራሽ ያደረገው ስብሰባ ከፊል ገፅታ አንድ

$
0
0
↧
↧

ኦህዴድ ኢሳትን ለማስቆም እንደሚሰራ አስታወቀ

$
0
0

ኢሳት ቴሌቪዥን

ኦህዴድ ኢሳትን ለማስቆም እንደሚሰራ አስታወቀ

eprdf_repsነሃሴ ፮(ስድስት)ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ሰሞኑን የድርጅቱ ከፍተኛ አመራሮች በነቀምት ባደረጉት ስብሰባ ህዝቡ ኢሳትን እንዳይመለከት ካድሬዎች ከፍተኛ ስራ መስራት እንደሚገባቸው አሳስበዋል።
አመራሮቹ ኢሳት የአሸባሪ ድርጅቶች ንብረት በመሆኑ፣ ህብረተሰቡ ኢሳትን መመልከቱን እንዲያቆም ባለስልጣኖቹ ወትውተዋል።
በስብሰባው ወቅት ለካድሬዎች ከተነገራቸው ነገር መካከል አንዱ ኢሳትን በሚመለከት ህግ ሊወጣ ነው መባሉ ነው። ምን አይነት ህግ እንደሚወጣ ግን ባለስልጣኖቹ ከማብራራት ተቆጥበዋል።
ኢሳት በናይልሳት የሚያሰራጨው ስርጭቱ በአፈና እንዲቋረጥ ከተደረገ በሁዋላ ላለፉት 7ወራት በኤስ ኢ ኤስ 5 እና በአሞስ ላይ የቴሌቪዥን ስርጭቱን እንዲሁም በተለያዩ የሬዲዮ ሞገዶች የኢትዮጰን ህዝብ እያገለገለ ይገኛል።

↧

Hiber Radio: በኢትዮ- ኬኒያ ድንበር ላይ ውጥረት ነግሷል

$
0
0

ጋዜጠኛ ሃብታሙ አሰፋ

ጋዜጠኛ ሃብታሙ አሰፋ

ህብር ሬዲዮ ዕሁድ   ነሐሴ 5 ቀን 2005 ፕሮግራም

<<…በቤኒን መስጊድ ተቃውሞ ላይ ተሳትፌያለሁ።ባንዲራ ያቃጠለ የለም።የሰሩት የተቀነባበረ ድራማ ነው።ያቆሙት የተሰበረ ታክሲ ሁሉ ድራማ ነው።ፊልሙን ልብ ብሎ ላየው በአንዋር መስጊድ ከተቀረጸ ተቃውሞ  ሆን ተብሎ የተቀናበረ  ነው። ሕዝቡ ሙስሊሙም ሆነ ክርስቲያኑ ተንኮላቸውን ተረድቷል። የሸሪያ መንግስት ይቋቋም ብሎ የጠየቀ የለም።የተጠየቀው ቀላል  ጥያቄ ነበር።ቀላል መልስ ነው ያለው። ይሄ ሁሉ ሽብር አያስፈልገውም…  በወሰዱት የጭካኔ እርምጃ በርካታ ንጹሃን ላይ ጉዳት አድርሰዋል።በሺህ የሚቆጠሩ ታስረዋል።የኔም  አባትና ወንድሜ ታስረዋል።ይሄ ግፍ ነው።ይንን ሁሉም ሊቃወመው ይገባል…መጅሊሱ ውስጥ መንግስት ያስቀመጣቸው አንዳንዶቹ ለሕይወታችን ፈርተን እንጂ እየተደረገ ያለውን አንደግፍም የሚሉም አጋጥመውኛል…>>

አቶ አክመል ሸሪፍ የቬጋስ የሙስሊሞች ኮሙኒቲ ዋና ጸሐፊ በቅርቡ ከአገር ቤት እንደመጡ ከሰጡን ቃለ ምልልስ የተወሰደ (ሙሉውን ያዳምጡት)

<<…እኔም ትራይቮን ማርቲን ነኝ  ብዬያለሁ። ለሴነተሮች፣ለኮንግረስ ይሄ ራስን መከላከል በሚል ከለላ የተቀመጠ ሕግ እንዲሻሻል የበኩላቸውን እንዲያደርጉ ጠይቄያለሁ። የሟቹን ምስል የያዘ ካኔተራ ለብሼ በአደባባይ አዎ እሄዳለሁ። የሚደግፉም ደስ የማይሰኙም አሉ…>>

የሎስ አንጀለስ ነዋሪ የሆኑት አቶ ሰለሞን ኢኢዮ አሜሪካውያን የመብት ጥሰት ሲያዩ ዝምታ አያዋጣም ይላሉ(ቆይታ አድርገናል)

ሙጋቤ በዓለም ላይ ረጅም ዘመን ስልጣን ላይ ያሉ መሪ ናቸው።33 ዓመት ስልጣን ይዘው በ89 ዓመታቸው ለአምስት ዓመት ተመርጫለሁ ብለዋል። የአፍሪካ አምባገነኖች የተለማመዱት የሚመስለው የምራባውያን ወቀሳዎች እና የአፍሪካውያን አቻዎቻቸው ተራ ሽመንገላዎችን እያስተናገዱ ነው። የሳቸው ተመርጫለሁ ማለትን ተከትሎ የተጀመረው የቃላት ጦርነት ወደ ከፋ ደረጃ ይቀጥል ይሆን? (ልዩ ዘገባ)

ተጨማሪ ቃለ መጠይቆች ተካተዋል

ዜናዎቻችን

በኢትዮ- ኬኒያ ድንበር ላይ ውጥረት ነግሷል

ኬኒያ አራት ፖሊሶቿን በታጣቂዎች ጥቃት አጣች

በኢትዮጵያ ሰሞነኛው እስራት ወደ ጋዜጠኞቹም ዞሯል

ሁለት ጋዜጠኞች ከሙስሊም ጉዳዮች ጋር በተያያዘ አ/አበባ ውስጥ ታሰሩ

በሙስሊሙ ህ/ሰብ ላይ እየተወሰደ ያለው የሀይል እርምጃ ከተለያዩ አቅጣጫዎች ተቃውሞ አስከትሏል

በአፈሳ ከታሰሩት ውስጥ ጥቂቶች እየተለቀቁ ነው

በድብደባ ከፍተኛ ጉዳት የደረሰባቸው ሰዎች ፎቶ ግራፎች ይፋ መሆን ቀጥሏል

በስራ ማቆም አድማ ላይ ያሉ የቬጋስ ታክሲ አሽከርካሪዎች ይግባኝ ውድቅ ሆነ

አንድነት በአዲስ አአበባ የተሳካ ሕዝባዊ ስብሰባ አደረገ

የታሰሩ አባሎቹና አመራሮቹ በፖሊስና ደህንነቶች ጫና በሀሰተኛ ክስ ላይ እንዲፈርሙ እየተገደዱ ነው

ሌሎችም ዜናዎች አሉን

↧

የሚኒሶታው ሪሳላ ኢንተርናሽናል በምዕራብ አርሲ፣ በኮፈሌና አከባቢዋ መንግስት በሙስሊሞች ላይ የፈጸመው ግድያ እንዳስቆጣው ገለጸ

$
0
0

Risala International
በምዕራብ አርሲ ዞን በኮፈሌና አከባቢዋ በሙስልሙ ማህበረሰብ ላይ የደረሰውን ግደያ እስራትና እንግልት ለመቀወም የወጣ የአቋም መግለጫ፨
ሪሳላ ኢንተርናሽናል ሚኒሶታ
በሃገራችን ሙስሊም ማህበረሰብ የምፈጸምበትን የሃይማኖትና ሰብአዊ የመብት ጥሰት ለመቀወም ሰላማዊ ትግል ከጀመረ ሁለት አመታት ተቆጥረዋል። በዚህ ህደት ዉስጥ ህብረተሰቡ ፊጹም ሰላማዊነቱንና ህጋዊነቱን ጠብቆ ይገኛል።በተቃራኒው የመንግስትን ስልጣን የተቆጣጠረው ወገን በተደጋጋሚ የመብት ጥሰትን ሲያከናዉን ማያቱ የተለመዳ ክስተት ሆኗል ።ከቅርብ ግዜ ወዲህ መነግስት ተብየው አካል በገርባ፣ በአሳሳ፣በሀረር፣ ያደረሰዉን ግድያና በተለያዩ አካባቢዎች የማፈጸመው እስራትና እንግልት ከመጠኑ ያለፈና በመህበረሰባችን ላይ ከፍተኛ ጉዳት በማድረስ ላይ ይገኛል። በሙስሊሙ የቀረበው ህጋዊና ህገ መንግስታዊ የመብት ጥያቄ ግልጽ እና በቀላሉ ምላሽ ሊሰጠው የሚገባው ሆኖ ሳላ በመንግስት እየተገበረ ያለው ግን ወደማይፈለግ ግጭትና ያለመረጋጋት አቅጣጫ የሚወስድ እጅግ አሳዛኝና ሃላፊነት የጎደለው ተግባር ነው። በአሁኑ ወቅት በምዕራብ አርሲ በኮፈሌና አከባቢዋ የበርካታ ሙስሊም ወገኖቻችን በአሰቃቂ ሁኔታ ሞት የአካል ጉዳትና እንግልት በመንግስት ታጣቂ ሀይሎች መፈጸሙ እጅጉን አስቆጥቶናል።
ይህም የስርዓቱን ማንነት ለመላው ዓለም በግልጽ የሚያሳይ ነው።እኛም በሚኒሶታና አካባቢዋ የምንገኝ ሙስሊሞች ይሄን አሰቃቂ ተግባር በጥብቅ እያወገዝን ሰላምና ዲሞክራሲ ወዳድ የሆኑ ወገኖች ሁሉ ይህን ኢሰብኣዊ ድርጊት ከጎናችን ሆነው እንዲቀወሙ ጥሪኣችንን እናቀርባለን። በተጨማሪም የሀገርን ሉዓላዊነትን ለማስከበር የተዋቀረው የመከላከያ ሰራዊት በወገኑ ላይ በዚህ መልኩ መዝመቱን አጥብቀን እናወግዛለን።
በዚህ የግፍ ጭፍጨፋ ህይወታቸውን ያጡትን ሰመዕታት(ሸሂድ)ወገኖቻችንን በከፍተኛ ሀዘን እየዘከርን ፈጣሪ አላህ ነፍሳቸውን በጀነቱል ፍርደውስ እንድያኖርልን እንጠይቃለን።ለሟችና ተጎጂ ቤተሰብን ፈጣሪ አላህ መጽናናቱን እንድሰጥልን እንለምናለን።በዚህ አጋጣሚ ይህን መሰረታዊ የሀይማኖት መብት ለማስከበር እየታገላ ላሉት ወገኖቻችን የሚያሳየው የአላማ ጽናትና ቆረጥነት ከልብ አርክቶናል።ህዝባዊ ትግሉንም በተገቢ ስልትና ድሲፕሊን እየመራ ያለው ድምጻችን ይሰማ በሚሰጠው በሳል አመራር አድናቆታችን ከፍተኛ ነው።በመጨረሻም ሪሳላ ኢንተርናሽናል በመንግስት ስልጣን ለያዘው አካልና ለመላው ማህበረሰባችን የሚከተለውን ጥሪ ያስተላልፋል።
• ያላ አግባብ በግፍ የተገደሉ ወገኖቻችንን አስመልክቶ የግድያ መንስኤና ፈጻሚ በገለልተኛ ወገን ተጣርቶ በአጥፍወች ላይ ህጋዊ እርማጃ እንድወሰድ አጥብቀን እንጠይቃለን።
• በሙስሊሙ ላይ በዘመቻ መልክ የተከፈተው ግድያ፣እስራት፣ግርፋት፣የእምነት መዕከል የሆነውን መስጊድ መድፈር፣ያላ ህጋዊ ፈቃድ የግለሰብ ቤት መፈተሽ፣ወዘተ የመሳሰሉት ህገወጥ ድርጊቶች ቤስቸኳይ ቁመው ህብረተሰቡ በነጻነት እምነቱን እና እለታዊ ኑሮውን እንዲመራ እንዲደረግ አበክረን እናሳስባለን።
• ያላ አግባብ የታሰሩት የመፍትሄ አፈላላጊ ኮምቴ አባላት በተለየዩ የሀገሪቱ ክልሎች በስፋት የታገቱ ሙስሊሞች በሙሉ ያለ ምንም ቅድመ ሁኔታ በነጻ እንድፈቱ እንጠይቃለን።
• የሙስሊሙ ማህበረሰብም የጀመረውን ሰላማዊ የመብት ማስከበር ትግል ድምጻችን ይሰማ በሚያስተላልፈው በሳል አመራር በመከተል አጥብቆ እንዲገፉበት እያሳሰብን ለዚህም የፈጣርያችን እገዛ እንዳይለየው የዘወትር ጻሎታችን ነው።
• በውጭ የምንገኝ ሙስልሞች ከመቼውም ግዜ ይበልጥ በኣንድነት ተቀናጅተን ስልት በመንደፍ ተጨባጭ ተግባራትን ማከናወን የሚገባን ስለሆና በአላህ ስም ለሁሉም ወገን የትብብር ጥሪኣችንን እናስተላልፋለን።
ኢስላም የሰላም ሀይማኖት ነው።
አንድነታችን ሀይላችን ነው።የህዝብን ሰብኣዊ መብት በግፍ ግድያና በማሸበር ማፈን አይቻልም።
መንግስታዊ አሸባሪነትን እናወግዛለን።
በሃይማኖት ጉዳይ አሁንም የመንግስት ጣልቃ ገብነት ይቁም።
አላሁ አክበር አላሁ
አክበር አላሁ ኣክበር !!!

↧
Viewing all 15006 articles
Browse latest View live