Quantcast
Channel: Ethiopian News | ዘ-ሐበሻ | Latest News Provider | News For All
Viewing all 15006 articles
Browse latest View live

በሞስሊሙ ማኅበረሰብ መሪዎች ላይ የተወሰነውን እስራት ሸንጎ ያወግዛል።

$
0
0

ሐምሌ 29፣ 2007 (ኦገስት 5፣ 2015)

shengoሰኞ  ሐምሌ 27፣ 20017  (ኦገስት 3፣ 2015) በሞስሊሙ ማኅበረሰብ መሪዎች ላይ የህወሓት/ኢህአዴግን ፍላጎት በማስፈም የሚታወቀው ፍርድ ቤት ከሰባት ዓመት እስከ 22 ዓመት የሚደርስ እስራት እንደበየነባቸው ይፋ ሆኗል።

የሞስሊሙ ኅብረተሰብን የተቃውሞ ድምጽ መረት በማድረግ በሰላማዊ መንገድ መፍትሄ በማፈላለግ ተግባር ላይ ተሰማርተው የነበሩት እነአቡበከር አህመድ የታሰሩት ከሁለት ዓመት በፊት የህወሓት/ኢህአዴግ መንግሥት በሙስሊሙ ማኅበረሰብ እምነት ውስጥ ጣልቃ በመግባት አመራሩን ለመቆጣጠርና እሱ የሚፈልገውን የእምነት ፈርጅ ኢትዮጵያውያን  ሞሰሊሞች በግዴታ እንዲቀበሉ ያውጠነጠነውን ሃላፊነት የጎደለው ተግባር እምቢ ማለታቸውን ተከትሎ እንደነበር ይታወሳል።

ሸንጎና ሌሎችም እጅግ በርካታ ኢትዮጵያውያን በሀገራችን ውስጥ የሞስሊሙ ማኅበረሰብ መንግሥት በሃይማኖቱ ውስጥ እንዳይገባ ያቀረበውን ጥያቄ በማክበር እጁን እንዲያነሳ በተደጋጋሚ ሲያሳስብ ቆይቷል።  ሆኖም እንደተለመደው ሁሉ ከራሱ ሌላ ማንንም ማዳመጥ ያልለመደው  የህወሓት/ኢህአዴግ ጆሮ ዳባ ልበስ በማለት ሃላፊነት የጎደለው እርምጃ በሚቆጣጠረው ፍርድ ቤት በኩል ተግባራዊ እንዲሆን አድርጓል።

ይህ እርምጃ የሞስሊሙን ኅብረተሰብ የሃይማኖት ነፃነት ጥያቄ ይበልጥ ያጠናክረዋል እንጂ  አያዳክመውም። እንዲያውም የሞስሊሙ ብረተሰብ አባላትና ሌሎችንም በህጋዊና ሰላማዊ መንገድ ጥያቄን አቅርቦ በሕግ መብትን ማስከበር አይቻልም ወደሚል መደምደሚያ እንዲደርሱና አላስፈላጊ በሆነ ጎዳና እንዲጓዙ የሚገፋፋ ነው። ይህ ለሀገራችን ሰላምና መረጋጋት የሚረዳ ሳይሆን አደጋን የሚጋብዝ እጅግ ሃላፊነት የጎደለው እርምጃ ነው።

ሸንጎው በሞስሊሙ ኅብረተሰብ በመፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ አባላት ላይ የህወሓት/ኢህአዴግ መንግሥት የፖለቲካ መሳሪያ የሆነው ፍርድ ቤት የወሰደውን እርምጃ አጥብቆ ያወግዛል። የሞስሊሙ ኅብረተሰብም መሰረታዊ መብቱን በሰላማዊ መንገድ ለማስከበር በሚያደርገው እንቅስቃሴ የትግል አጋርነቱን ያረጋግጣል።

ኢትዮጵያውያን ሁሉ ህወሓት/ኢህአዴግ የሚያካሂደውን በሃይማኖት ነፃነት ላይ ያነጣጠረውን ጥቃት እንዲያወግዝ  ሸንጎ  ጥሪውን ያቀርባል። የህወሓት/ኢህአዴግ ደጋፊዎችም አገዛዙ ከቀን ወደቀን ሀገራችንንና ሕዝባችንን ወደተባባሰ አደገኛ ጎዳና መውሰዱን እንደቀጠለ መሆኑን እንዲገነዘቡ እያሳሰበ፡ በዚህም ምክንያት ለሚከተል አለመረጋጋት ተጠያቂው ህወሓት/ኢህአዴግ እንደሆነ ሁሉም እንዲገነዘበው እናሳስባለን።

ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!


የአርበኞች ግንቦት 7 አመራር ኤፍሬም ማዴቦ አስመራ ወርደው የትጥቅ ትግሉን ተቀላቀሉ

$
0
0

የአርበኞች ግንቦት 7 አመራር ኤፍሬም ማዴቦ አስመራ ወርደው የትጥቅ ትግሉን ተቀላቀሉ
(ዘ-ሐበሻ) ከአርበኞች ግንቦት 7 ከፍተኛ አመራሮች መካከል አንዱ የሆኑት አቶ ኤፍሬም ማዴቦ አስመራ ሄደው የትጥቅ ትግሉን መቀላቀላቸው ተሰማ::

የአርበኞች ግንቦት 7 መሪ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ እንዲሁም አቶ ነአምን ዘለቀ አስመራ ወርደው ትግሉን ከተቀላቀሉ ሳምንታት የተቆጠረ ሲሆን አቶ ኤፍሬም ማዴቦም ከትናንት በስቲያ ትግሉን ተቀላቅለዋል::

አርበኞች ግንቦት 7 በሕወሓት መንግስት ሠራዊት ላይ በሰሜን በኩል ጥቃት መሰንዘሩን ተከትሎ አፍቃሬ ወያኔ ሚዲያዎች በሰሜን በኩል ትግል የለም ለማለት “የኢትዮጵያ መንግስት ሰራዊቱን ወደ ሱማሊያ አሰማራ” የሚሉ ዜናዎችን በማስተጋባት ላይ ይገኛሉ::

ለዘ-ሐበሻ የደረሰው መረጃ እንደሚያመለክተው ከአቶ ኤፍሬም በተጨማሪ ሌሎች ስማቸው ያልጠቀሰ የድርጅቱ አመራሮች ትልቅ ገቢ የሚያስገኝላቸው ሥራቸውን እና ቤተሰቦቻቸውን በመተው የትጥቅ ትግሉን ተቀላቅለዋል::

የዛሬ 25 ዓመት ወደ ስደት ገብተው በሰሜን አሜሪካ የተለያዩ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የተማሩት አቶ ኤፍሬም ከጆርጅ ሜሰን ዩኒቨርሲቲ በማዕረግ የተመረቁ ታዋቂ የፖለቲካ ሰው ናቸው::

Health: ባለትዳር መሆን የተሻለ ጤንነት እንዲኖረን ያደርጋል?

$
0
0

wedding copy

ባህላዊ ዕውቀትም ይሁን ዘመናዊ ሳይንስ ያገቡ ሰዎች ከወንደላጤዎች የተሻለ ረጅም ዕድሜ እና ጤንነት እንዳላቸው ይገልፃሉ፡፡

“ከላጤዎች ጋር ሲነፃፀር ባለትዳሮች ጤናማዎችና እና ለረጅም ዘመን ለመኖር የታደሉ ናቸው” ይላሉ በካሊፎርነያ ዩኒቨርስቲ ሳይኮሎጂስት የሆኑት ዶክተር ቴዎዶር ሮቤልስ፡፡ “ጥናቶች እንደሚያሳዩት ባለትዳሮች በተለይ ወንዶች ረዘም ላለ ዕድሜ ይኖራሉ፡፡ በልብ በሽታዎች የተነሳ የመሞት ዕድላቸው ከላጤዎች ሲተያይ ያነሰ ነው፡፡ ጤናማ ሰዎች ትዳር የመመስረት ፍላጎት አላቸው” በማለት ትዳር ጤናማ የማድረግ አቅም እንዳለው ይገልጻሉ፡፡
“የሚረዳዱና የሚተጋገዙ ጥንዶች ጤናማነታቸው ከግንኙነታቸው ጋር ተያያዥነት አለው” ይላሉ የኦሃዮ ስቴት ዩኒቨርሲቲ ባልደረባዋ ዶክተር ጃኒስ ኪኮልት ግላሰር፡፡
ትዳር ለጤና በምክንያት
የጥሩ ባህርይ ባለቤት ያደርጋል

ጥንዶች በትዳር ሲጣመሩ በአደንዛዥ ዕፅ፣ በሲጋራ፣ እና በሌሎች ለጤና ጎጂ በሆኑ ነገሮች የሚደርሰባቸው ጉዳት እየቀነሰ ይሄዳል፡፡
“አብረው ለመኖር ሲስማው በፈቃደኝነትም ይሁን በትዳር አጣማሪያቸው ጉትጎታ ከነዚህ ሱሶች ስለሚታቀቡ ወይንም አወሳሰዳቸውን ስለሚቀንሱ የሚከሰት ነው” ይላሉ በኦሃዮ ስቴት ዩኒቨርሲቲ ሳይኮሎጂስት እና ተመራማሪ የሆኑት ዶክተር ክርስቶፈር ፍገንደስ፡፡

ማህበራዊ ግንኙነት

“ባለትዳር ከሆንክ/ሽ እስከ አሁን ከፈጠርካቸው/ ሻቸው ግንኙነቶች በጣም መቀራረብ የሠፈነበት እንደሆነ ትረዳለህ/ሽ፡፡ ይህ ማለት በማንኛውም ወቅት የምትፈልገውን/ጊውን እገዛ እና ድጋፍ ሊያደርግልህ/ ሽ የሚችል ሰው አለህ/ሽ ማለት ነው፡፡” ይላሉ ዶ/ር ጃኒስ፡፡
“በሌላ በኩል ደስተኛ ያልሆኑ ሰዎች ከማህበራዊ ኑሮ የተገለሉ ይሆናሉ፡፡ ይህም ወደ ድብርት ይመራቸዋል፡፡ የጤንነታቸውን ሁኔታም አይከታተሉም” ሲሉ በኒው ዮርክ ዩኒቨርሲቲ ሳይኪያትሪስት የሆኑት ዶክትር ሱዴፕታ ቫርማ ይናገራሉ፡፡

ጤናማ ልምዶችን ያዳብራሉ
ባለቤትዎ ጤናማ ልምዶችን እንዲያዳብሩ ሊረዱዎ ይችላሉ፡፡ “ባለቤትዎ በእርስዎ ባህርይ ላይ ከፍተኛ ተፅዕኖ ያሳድራሉ፡፡ ይህን መመገብ የለብህም/ሽም፤ አልኮል ቀንስ/ሺ ወዘተ የሚሉት ከዚህ በጎ ተፅዕኖ የሚመነጩ ናቸው” ይላሉ ዶክተር ቴዎዶር ሮቤልስ፡፡

ከዚህ በተጨማሪም በትዳራቸው ደስተኛ የሆኑ ሰዎች የዶክተሮቻቸውን ትዕዛዝ እንደሚያከብሩ አንድ ጥናት ይገልፃል፡፡
ከሚወዱት ሰው ጋር ለረጅም ጊዜ መኖርዎ ሌሎች የጤና ጠቀሜታዎችም አሉት፡፡ “አብዛኞቻችን ከፍቅረኞቻችን ጋር ለመዝናናት መኖራችን በጎ ጎን አለው፡፡ በትዳር ተጣምሮ መኖር ከሚያስገኘው ጋር ሲወዳደር ግን አነስተኛ ነው” ዶክተር ክርስቶፍር “ከትዳር የምናገኘው ፍቅርና መተጋገዝ ለራሳችን የምንሰጠውን እንክብካቤ እንዲጨምር ያደርጋል፡፡ ይህ የሚሆነው የትዳር ተጣማሪያችን በኛ ደስተኝነት ላይ የማይተካ ሚና ስላለው ነው” በማለት ዶክተር ቫርማ የትዳር ጥቅም ከፍተኛ እንደሆነ ይገልፃሉ፡፡
ቀለበት ማጥለቅ ብቻውን በቂ አይደለም፡፡ የተሻለ ትዳር ማለት የተሻለ ጤና ማለት ነው፡፡ የልብ ቀዶ ጥገና ከተደረገላቸው በሽተኞች ውስጥ በጥሩ ትዳር ውስጥ ያሉት የመዳን ዕድላቸው ከሌሎቹ የተሻለ እንደሆነ ከ15 ዓመታት በላይ የተካሄደ አንድ ጥናት ያስረዳል፡፡ ፍቅርና ደስታ በራቀው ትዳር ውስጥ የሚኖሩ በሽተኞች የመዳን እና በቶሎ የማገገም ዕድላቸው ዝቅተኛ እንደሆነም ጥናቱ ሳይጠቅስ አላለፈም፡፡

ለዚህ የተሰጠው ዋነኛ ምክንያት መጥፎ ትዳር ለከፍተኛ ጭንቀት የሚዳርግ በመሆኑ ነው፡፡ ይህ ደግሞ የበሽታ መከላከል አቅምን ክፉኛ ያዳክማል፡፡ በተለየ ሴቶች ለዚህ ዓይነቱ ጭንቀት ተጋላጭ ናቸው፡፡ በትዳር ላይ በሚጋጥም ጥላቻ (ያለ መወደድ ስሜት) ሴቶቹ ስሜተ ስስ መሆናቸው ለችግር አጋልጧቸዋል
ይላሉ ዶክተር ጃኒስ፡፡

ዶክተር ጃኒስ እና የጥናት ቡድናቸው በምርመራክፍሎች ውስጥ ጥንዶች ባስቀመጡት ስውር ካሜራ ሲጨቃጨቁ ሁኔታውን በመቅረፅ ለማጥናት ሞክረዋል፡፡ “በክርክርና ባለመስማማት ወቅት ጥላቻን የሚያሳዩ ጥንዶች ጭንቀትን የሚያባብሱ ሆርሞኖች መጨመር ታይቶባቸዋል፡፡ የቃላት መቋሰሉ ከፈጠረው ህመም ለመዳንም ብዙ ጊዜ ይወስድባቸዋል” ብለዋል፡፡
ጠቅለል ተደርጐ ሲቀመጥ ከባድ የትዳር ችግር ያለባቸው ሰዎች የበሽታ መከላከል አቅም ሊዳከም ይችላል፡፡ የትዳር የጤናማነት ሁኔታ ወንዶችንም የጤና ችግር ሊያስከትልባቸው ይችላል፡፡

“በጥናታችን እንደደረስንበት ከሆነ ድብርት፣ አለቅጥ ክብደት መጨመር እና ከፍተኛ የደም ግፊት ደስተኛ ባልሆነ ትዳር ውስጥ በሚኖሩ ሴቶች ላይ ይታያሉ፡፡ ነገር ግን ወንዶች ትዳራቸው በሚፈጥርባቸው ብስጭት የአደንዛዥ ዕጾች ሱሰኛ ከሆኑ ተመሳሳይ የጤና ጉድለት ሊያገጥማቸው ይችላል” ሲሉ ዶክተር ቫርማ የችግሩን ስፋት ያስረዳሉ፡፡ እንደሳቸው እምነት ሁለቱም ፆታዎች ደስታ የራቀው ትዳር በሚያስከትላቸው አለመመቸቶች ይጠቃሉ፡፡ ይሁንና የሚያሳዩት የጉዳት መጠን ግን የተለያየ ነው፡፡
ብቸኞች

አንድ ሰው ብቸኛ (single) ነው ሲባል ከሌሎች ጋር የቅርብ ወዳጅነት መመስረት አይችልም ማለት አይደለም፡፡ ሌሎች ደግሞ ለፍቅር የሚሆናቸውን ሰው ባለማግኘታቸው ብቸኛ ሊሆኑ ይችላሉ፡፡ ለዚህ ዋነኛው መፍትሔ ጥሩ ጓደኞችን ማፍራት ነው፡፡ እነዚህ ሰዎች ሊያስቡልዎና ሊጠነቀቁልዎ እርስዎም ተመሳሳዩን ሊያደርጉላቸው ይችላሉ፡፡ ይህ ዓይነቱ ራስን በጥሩ ሰዎች መሃከል ማኖር ትዳራቸውን በፍቺ ለበተኑ ሰዎችም ይሠራል፡፡

ፍቺ ካለዕድሜ ከመሞት ጋር ተያያዥነት እንዳለውና በተለይ በወንዶች ላይ በስፋት እንደሚታይ የአሪዞና ዩኒቨርሲቲ ባልደረባ የሆኑት ዶክተር ዴቪድ ስባራ ይናገራሉ፡፡ “በዕድሜ በሰል ካሉ ሰዎች ውስጥ ከፍቺ በኋላ በደስታ የተሞላ ህይወት ሲመሩ የሚታዩ ይኖራሉ፡፡ ደስታ በራቀው ትዳር ውስጥ ካሉና ትዳርዎ እንዲሠራ የሚችሉትን ያህል ከለፉ በኋላ ተስፋ እንደሌለው ካወቁ ፍቺ ምክንያታዊና አምነን መቀበል ያለብን አማራጭ ይሆናል፡፡ ተፋትተው ደስተኛ ሆነው መኖር ከቻሉ ፍቺ የሚያመጣቸው ጐጂ ጐኖች ሊያሳስብዎ አይገቡም” ይላሉ ዶክተር ዴቪድ፡፡

ከፍቺ በኋላ ሴቶች ከወንዶች በተሻለ መልኩ ጥሩ ስሜት ሊሰማቸው ይችላል፡፡ “ላጤዎችን እና የጤናቸውን ሁኔታ ስናይ ሴቶቹ ከወንዶቹ በተሻለ ጤንነት ላይ ይገኛሉ፡፡” የሚሉት ዶክተር ክርስቶፈር ባለትዳሮች ወይንም አብረው የሚኖሩ ፍቅረኞች ለመስማማት በማይችሉበት ወቅት በአክብሮት ያለ ዘለፋ እንዲነጋገሩ ይመከራል፡፡ ጥላቻ በከፍተኛ ሁኔታ የሚንፀባረቅበት ክርክርና ጭቅጭቅ ለጤና ጉዳት ያጋልጣል፡፡ በተገቢው ሁኔታ መነጋገር ሲባል ማዳመጥ፣ መስጠት፣ ቅድሚያ መስጠት እና የተናጋሪውን ስሜት መረዳትን ያጠቃልላል፡፡ በሰው ልጆች ውስጥ ያለው ትልቁ ፍላጐት ለመወደድ መንሰፍሰፍ ሲሆን እውቅና ማግኘት ደግሞ ሌላው ነው፡፡ ይህን ካደረጉ “እያዳመጥኩህ/ሽ ነው” የሚል መልዕክት ያስተላልፋሉ፡፡ ይህ አይነቱ መተሳሰብ የትዳር ችግሮቻችሁን በቀላሉ ለመፍታት እና ለመስማማት ያስችላችኋል፡፡

ይህ ጽሑፍ በአዲስ ጉዳይ መጽሔት ላይ ታትሞ ወጥቶ ነበር

ኢህአዴግ በኤርትራ አራት አቅጣጫዎች ጥቃት ሊሰነዝር ማሰቡ ተዘገበ

$
0
0

በቅርቡ የተጠናከረ እንቅስቃሴ የጀመረው የአርበኞች ግንቦት ፯ ኃይል በተደጋጋሚ በሚያወጣው መረጃ በተለያዩ ቦታዎች ጥቃት ማድረሱን በይፋ ቢገልጽም ኢህአዴግ ጥቃቱን በቀጥታ ለማስተባበል እስካሁን አልወደደም። ይሁን እንጂ አቶ ሃይለማርያም ደሳለኝ “ህዝብ አስፈቅደን” ሲሉ ኤርትራን እንደሚወጉ ይፋ አድርገዋል። አብዛኞች እንደሚስማሙበት ዛቻው ግጭት ስለመኖሩ የሚያረጋግጥ ነው። በሌላው አንጻር ደግሞ ይህንን የሃይለማርያም ንግግር የኤርትራው ሹም በዓለምአቀፍ መድረክ ላይ የተለመደ የህወሃት/ኢህአዴግ ማስፈራሪያና ዛቻ በማለት አጣጥለውታል፡፡
front ertria
የግጭቱን ደረጃና በኢህአዴግ ላይ የደረሰውን የጉዳት መጠን ኢሳት ይፋ ካደረገበት ጊዜ ጀምሮ ኤርትራን መውቀሰና ማስፈራራት የጀመረው ኢህአዴግ፣ ቀጣናው ሊተራመስ እንደሚችል ስጋቱን ገልጾ ኤርትራን ለመደብደብ የሚያስችለውን ፈቃድ ስለማግኘቱ ጎልጉል መረጃ ደርሶታል። በአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መ/ቤት (ስቴት ዲፓርትመንት) አራተኛዋ ሹም ዊንዲ ሼርማን ግንቦት ፯ን በስም በመጥቀስ በተቃወሙ ማግስት የባለሥልጣኗን የድጋፍ ቃል አስመልክቶ ቴድሮስ አድሃኖም በኢህአዴግ በኩል ያለውን ውለታ ሲናገሩ “ለምንከፍለው ዋጋ መጠን ተመጣጣኝ ክፍያ ነው” ሲሉ ውስጡ በርካታ የፖለቲካ “ጥሬ ሃብት” የሞላበት አስተያየት ለዋልታ ኢንፎርሜሽን ማዕከል ሰጥተው ነበር።

የጎልጉል ታማኝ የመረጃ ምንጭ እንዳሉት ፕሬዚዳንት ኦባማ አዲስ አበባ በነበሩበት ወቅት የህወሃት ሰዎች ይህንኑ ጉዳይ በዋናነት አንስተው ነበር። ኢህአዴግ በሶማሊያ እያበረከተ ላለው ተግባር መሰናክል ተደርጎ የቀረበው የኤርትራ ተቃዋሚዎችን የመርዳት ጉዳይ እልባት እንዲበጅለት አሜሪካ ድጋፍ እንድትሰጥ የጠየቀው ኢህአዴግ፣ አሜሪካ ያሉ የከፍተኛ ተቃዋሚ አመራሮች ገደብ እንዲጣልባቸው ተማጽኗል። አሜሪካ ኢህአዴግ “አሸባሪ” ብሎ የሚፈርጃቸውን በሙሉ በሽብርተኛነት በመፈረጅ የመን የተጫወተችውን አይነት ሚና እንድትደግም ተጠይቃለች። ጥያቄው የቅዠትም ሆነ የምር፣ የግንቦት ፯ አመራሮች ነቅለው አስመራ መግባታቸው ጥያቄውን ዋጋ ቢስ አድርጎታል የሚሉ አሉ።

አሜሪካ የቀረበላትን ጥያቄዎች ስለመቀበሏ ያልጠቀሱት የመረጃው ባለቤቶች፣ ኤርትራ ውስጥ መተራመስ ሳይፈጠርና ክልሉና ቀጣናው ሳይናጋ ጥንቃቄ የተሞላበት ርምጃ ቢወሰድ አሜሪካ ተቃውሞ እንደማይኖራት ማረጋገጫ መስጠቷን አመልክተዋል። ይህ አቋም ኦባማ አዲስ አበባ ከመሄዳቸው በፊት በተለያዩ ደረጃዎች ተመክሮበት ከስምምነት የተደረሰበት ስለመሆኑም ገልጸዋል። ከዚህ አንጻር አቶ ስብሃት ነጋ “ከኤርትራ ጋር የሚካሄድ ውጊያ ጥንቃቄ ይጠይቃል” ሲሉ መናገራቸው ይታወሳል።

በዚሁ መነሻ ኢህአዴግ በጎንደር፣ በሱዳን ድንበር፣ በአፋርና በትግራይ የተለያዩ ግንባሮች ድንገተኛ ማጥቃት ለመሰንዘር በዝግጅት ላይ እንደሚገኝ ተጠቁሟል። ወቅቱ የዝናብ መሆኑ እንዳለ ሆኖ፣ ለዚሁ ጥቃት ሠራዊቱ የሚወጋው “ተቃዋሚ የሆኑ የራሱን ወገኖች ሳይሆን ሻእቢያን ነው” በሚል የማነቃቂያ ስራ እየተሰራ እንደሆነ የመረጃው ሰዎች ተናግረዋል። በድጋሚ የመሥራቱ ጉዳይ ገና ባይታወቅም ይህ አካሄድ በባድመ እንደተደረገው የወኔ ማነቃቂያ እና የውጊያ ሞራል ማነሳሻ ለማድረግ ታስቦ በጥናት የተደረገ ለመሆኑ የመረጃው አቀባዮች ያስረዳሉ፡፡ አያይዘውም “ጦርነቱ ኢህአዴግ ካሰበው ውጪ ባንድ በኩል ከተሰበረ በጦሩ ውስጥ የሚገኙ የሌሎች ኅብረተሰብ ክፍል አባላት የሆኑ ወታደሮች ሊከዱና የተቃዋሚ ኃይሎችን ሊቀላቀሉ ይችላሉ” የሚል ስጋት ስለመኖሩ ሪፖርት መቅረቡን ይጠቅሳሉ።

በመከላከያ ሠራዊት ውስጥ ያለው ሚዛን ያልጠበቀ የኃላፊነት ደረጃና የህወሃት አባላት ያላቸው የተጋነነ የበላይነት በመሃል አገር ከሚፈጸመው ረገጣ ጋር ተዳምሮ የተከማቸው ቅሬታ ሊፈነዳ ይችላል የሚል ጥርጣሬ እንዳለም እነዚሁ ክፍሎች ያስረዳሉ።

ኢህአዴግ የትጥቅ ትግል አውጀው ኤርትራ ከመሸጉና መሣሪያ አንግበው ትግል እያደረጉ መሆናቸውን ይፋ ካደረጉ ግንባሮች ሁሉ በድርጅታዊ አቅሙ ከፍተኛ የሚባለውን (ደሚት/ትህዴን) የትግራይ ህዝብ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄን እስካሁን በሽብርተኛነት አለመፈረጁ ይታወቃል።

Source: ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ

በቤተ ክርስቲያን የሀብት ምዝበራ የፈጸሙ በሕግ እንዲጠየቁ ፓትሪያርኩ መመሪያ ሰጡ

$
0
0

‹‹በመዝባሪ ላይ አልደራደርም፤ እስከ መጨረሻው ከፊት ለፊት ነኝ››

abune-matyas

ዛሬ በአዲስ አበባ ከተማ ታትሞ የተሰራጨው አዲስ አድማስ ጋዜጣ እንደዘገበው በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የአድባራቱን ሰፋፊ መሬቶችና የገቢ ማስገኛ ተቋማት እየመዘበሩ ራሳቸውን ያበለጸጉ የአስተዳደር ሓላፊዎች በሕግ እንዲጠየቁ ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ አቡነ ማትያስ መመሪያ ሰጡ፡፡
የአስተዳደር ሓላፊዎቹ የአድባራቱን ሰፋፊ መሬቶችና የንግድ ተቋማት ያለጨረታ ከገበያ ዋጋ በታች ከ15 ዓመት እስከ ዕድሜ ልክ በመዋዋል የቤተ ክርስቲያኒቱን ጥቅሞች አሳልፈው በመስጠት ራሳቸውን አበልጽገዋል- ተብሏል፡፡
ፓትርያርኩ መመሪያውን የሰጡት፣ ላለፉት ስምንት ወራት በሀገረ ስብከቱ አድባራትና አንዳንድ ገዳማት የመሬት፣ የሕንፃና የልዩ ልዩ ገቢ ማስገኛ ተቋማት ኪራይ ተመንን ሲያጣራ የቆየው ኮሚቴ ያዘጋጀው ጥናታዊ ሪፖርት ከጠቅላይ ጽ/ቤቱ የውሳኔ ሐሳብ ጋር ከትላንት በስቲያ ከቀረበላቸው በኋላ ነው፡፡
በፓትርያርኩ መመሪያ የተቋቋመው ኮሚቴው፣ በ51 አድባራት መሬት፣ ሕንፃና ሕንፃ ነክ ጉዳዮች ላይ ባካሔደው ጥናት የተጠቆሙት የመፍትሔ ሐሳቦችና በዋና ሥራ አስኪያጁ በብፁዕ አቡነ ማቴዎስ ሰብሳቢነት የሚመራው የአስተዳደር ጉባኤ የተስማማባቸው የመፍትሔ ሐሳቦች በሙሉ ተፈጻሚ እንዲኾኑ አቡነ ማትያስ ትእዛዝ ሰጥተዋል፡፡
በጥናቱ ሒደት የኮሚቴውን አባላት በጥቅም ለመደለል ከመሞከር ጀምሮ በማስፈራራትና ስም በማጥፋት የማጣራት ሥራውን ለማስተጓጐል ሲጥሩ የነበሩ ሐላፊዎች፣ በመፍትሔው አተገባበር ላይም ዕንቅፋት ሊፈጥሩ ይችላሉ ለሚለው ስጋት ፓትርያርኩ በሰጡት ምላሽ፤ ‹‹ወደ ኋላ ወደ ጎን የለም፤ ወደፊት ነው፤ በቤተ ክርስቲያን ሀብት ምዝበራ ከማንም ጋር አልደራደርም፤ ከጎኔ ኹኑ፤ እስከ መጨረሻው ከፊት ለፊት ነኝ›› ሲሉ በቁርጠኝነት ተናግረዋል፡፡
በጥናታዊ ሪፖርቱ እንደቀረበው፤ የገቢ ማስገኛ የንግድ ተቋማቱ፣ ከአዲስ አበባ የመሬት ገበያ አንጻር ሊታሰብ ከማይችልበት ዝቅተኛው በካሬ ሜትር 0.37 ሳንቲም፣ ከፍተኛው ብር 70 ያለጨረታ ከ15 ዓመት እስከ ዕድሜ ልክ የኪራይ ውል ተፈጽሞባቸዋል፡፡ ይህም ጥቂት ሙሰኛ የደብር ሓላፊዎችና ግለሰብ ነጋዴዎች ሚልየነር እንዲኾኑበት ዕድል በመስጠት ቤተ ክርስቲያኒቱን የበይ ተመልካች እንዳደረጋት ተገልጧል፡፡
የአድባራት አለቆች፣ ጸሐፊዎች፣ ሒሳብ ሹሞችና የሰበካ ጉባኤ አባላት በተገኙበት በተካሔደው ማጣራት ለጥናት ቡድኑ መረጃ በመስጠታቸውና ጥያቄ በማንሣታቸው ከመመሪያ ውጭ ከሓላፊነታቸው የታገዱት፣ የአራዳ ገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ደብር ዋና ተቆጣጣሪ መጋቤ ጥበብ ወርቁ  አየለና የደብረ ጽጌ ቅዱስ ዑራኤል ቤተ ክርስቲያን ዋና ሒሳብ ሹም ወ/ሮ መና የማነ ብርሃን ሥዩም ወደ ቀድሞ የሓላፊነታቸውና ቦታቸው እንዲመለሱ በአስተዳደር ጉባኤው ተወስኗል፡፡
የጠቅላይ ቤተ ክህነቱ የሕግ አገልግሎት መምሪያ፤ ሙሰኛ ሓላፊዎችን ለሕግ ከማቅረብ በተጨማሪ  የገቢ ማስገኛ ተቋማቱ ለሦስተኛ ወገን እየተላለፉ የተሰጡበትን ውሎች በመሰረዝ የቤተ ክርስቲያኒቱን ጥቅም የሚያስከብርና የሚያስቀድም ወጥ አሠራር እንዲዘረጋ ተወስኗል፤ ተቋማቱም በየአጥቢያው በተናጠል የሚተዳደሩበት አካሔድ ቀርቶ በማዕከል የሚመሩበት ሥርዐት እንደሚበጅ የተጠቆመ ሲኾን፤  ይህንንም የሚያስፈጽም ጽ/ቤትና ፓትርያርኩ የሚሰበስቡት ቦርድ እንደሚቋቋም ታውቋል፡፡
የፓትርያርኩ ልዩ ሀገረ ስብከት በኾነው አዲስ አበባ፣ ጥናቱ ባልሸፈናቸው ሌሎች አድባራትና ገዳማትም እንዲቀጥል አቡነ ማትያስ ያዘዙ ሲኾን በመጪው ዓመት ጥቅምት በሚካሔደው 34ኛው ዓመታዊ አጠቃላይ ሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤም በአገር አቀፍ ደረጃ እንዲተገበር በቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ እንዲወሰንበት እንደሚያደርጉም አስታውቀዋል፡፡

“ደሙን ሰጥቶ፣ አጥንቱን ከስክሶ ፣ የስኬት ማማ ላይ ያስቀመጣችሁ ጀግና ስርዓት ” ( ሄኖክ የሺጥላ )

$
0
0

Tensaye

በእውነት ወያኔ ምን በደለ ? እንደው ሀገር ባለማ ! ድልድይ በሰራ ፣ ግድብ በቆፈረ ! ውይ የሰው ነገር ! አሁን ማን ይሙት ወያኔ የደርግን ያህል ጨካኝ ሆኖ ነው እንዲህ የምትረባረቡበት ? እናንተ እኮ አታፍሩም ይሄኔ ፣ ከግድብ የመናገር ነጻነት ይቅደም ፣ ከውሃ ማቆር የሰው ልጆች እኩልነት ይቅደም ፣ ከልማታዊ አርሶ አደርነት የሰብአዊ ክብር ና የመንፈስ ልዕልና ይቅደም ፣ የተጻፈ ከማንበብ ( ዘላለማዊ ክብር ለክቡር ጥቅላይ ሚንስትር መለስ ዜናዊ የሚለውን አይነት ማለት ነው ) የመጻፍ መብት ይከበር ፣ በየመንገዱ ሥራ አጥቶ ከመደርደር ፣ የመሰለፍ መብታችን እውቅና ይሰጠው ፣ አስራ አራት ክልል በካርታ ላይ ከማስቀመጥ ፣ በፈለግነው ክልል ሄዶ የመስራት መብታችን ይጠበቅ ፣ የዜጎች እኩልነት በዜና እና በዝና ሳይሆን በነባራዊው ዓለም ፣ በለት ተለት ሕይወታችን ይተግበር እና ወዘተ ትሉ ይሆናል ።

በእውነት አታፍሩም ! አሁን እስኪ ማን ይሙት ፣ ድልድይ ይበልጣል ፣ የህዝቦች እኩልነት ? ለኛ የመጻፍ ነጻነት ይሻለናል ወይስ የማቃጠር መብት ? ዜጎች ደሞ እኩልነት ፣ እኩልነት ፣ እያላችሁ የምታላዝኑት ፣ እንኳንስ ይቅርና በዜግነት መብት በቁመት እኩል የሆኑ ሰዎች ማግኘት ዘንድሮ ቀላል ነገር ነው ወይ ? ደሞ በተወደደ ወረቀት መጻፍ ፣ መጻፍ ፣ መጻፍ ። አማራ ድሮም መጻፍ ይወዳል ! ክስ ይወዳል! ምናለ ባትጽፉ አትሞቱ ፣ እውነት ባትናገሩ አትሞቱ ፣ ስለ ሚኒሊክ ባትናገሩ አትሞቱ ፣ ስለ በላይ ዘለቀ ባታወሩ አትሞቱ ! አሁን የደደቢት ታሪክ አልበቃ ብሎ ነው አዳሜ የ አጼ ቴዎድሮስን ታሪክ የሙጥኝ ያለው ? አረ ምን እሱ ብቻ ፣ ሀገር ፣ ሀገር ፣ ሀገር ትላላችሁ ? ሀገር ምንድን ነው ? ባንዲራ ፣ ባንዲራ ፣ ባንዲራ ? ባንዲራ ድልድይ አይሆን ? ምንነት አይበላ ! ነጻነት አይሸጥ ። ይህ የአማራ ተረት ነው ። አሁን እስኪ ማን ይሙት ለኢትዮጵያ የሚጠቅማት ኮብል ስቶን ነው ወይስ አክትቪስት ? “እኛ ( ወያኔ-ትግሬዎች ) እኩል ሳትሆኑ እኩል አደረግናችሁ ፣ ከጨቋኝ ፊውዳል እጅ ታደግናችሁ ፣ ዛሬ በራሳችሁ ቋንቋ መናገር ስትችሉ ፣ የፈቀዳችሁትን ባንዲራ አወጣችሁ ፣ የብሔር ብሔረሰቦች መብት ያለገደብ ተከበረ ፣ ታዲያ ይሄም አልበቃም ብሏችሁ ፣ እኛ ታግለን ባመጣነው ፣ ስልጣን ላይ መቀመጥ አማራችሁ ? ” ።

ታዲያ ለምንድን ነው ይህን ” ደሙ ሰጥቶ፣ አጥንቱን ከስክሶ ፣ የስኬት ማማ ላይ ያስቀመጣችሁ ጀግና ስርዓት የምትፈታተኑት ? ” ተዉ ግን ፣ ተው ? እኔ ልሙት አሁን የወያኔ ጥፋቱ ምኑ ላይ ነው ? ይሄኔ እኮ << ምርጫ 100% አሸነፈ ፣ ነብዩን ገደለ ፣ የእስልምና ኮምቴዎችን አሰረ ፣ በስልጣን ላይ ያሉት አብዛኛው ካንድ ብሔር የተመረጡ ናቸው ፣ በዘር ተደራጅተው ሀገሪቷን ተቀራመቷት ፣ ወያኔ እጁ ላይ ደም አለ ፣ መንግስት ሳይሆን ቃሊቲ ( ዘብጥያ ) መውረድ ያለበት ስርዓት ነው ፣ ይህ ስርዓት ቢያንስ የቃልቻ ያህል እንኳ ለሀገር ሰላም አይጸልይም ፣ ይህ ስርዓት ሳይሆን የእባብ ስሪት ነው ” እና ወዘተ ትሉ ይሆናል ። ቆይ ቆይ << 17 ዓመት የታገለ ስርዓት አንድ ነብዩን ቢገል ምን አለበት ፣ ሀገር በማልማት ላይ ያለ መንግስት ፣ የህዝቡን ድምጽ ቢሰርቅ ምን አለበት ? ቆይ አሁን አባይን እየገነባ ያለ ኃይል ፣ መጅሊስን ቢያፈርስ ያን ያህል መጅሊስ ትልቅ ነገር ሆኖ ነው ፣ እንኳን መጅሊስ << ቲዊን-ታወር ፈርሶ የለም እንዴ ? >> ። ደሞ- መጅሊስ መጅሊስ አትበሉ ፣ በየሰፈሩ ህውሃት መጅሊስ አረቢ አስነጥፎ ሺሻ ያለገደብ እንዲገባ ያደረገውን ረስታችሁ ነው ስለሌላው መጅሊስ የምታወሩት ? ምን ታካብዳላችሁ ? ደሞ ተቃዋሚ የምትባሉት ሁሉ ትልቁ ችግራችሁ ምን እንደሆነ ታውቃላችሁ ? ትልቁ ችግራችሁ ንገረኝ ካላችሁ << ወሬኞች ናችሁ !>> እኛ ደሞ በወሬ አንፈታም ። አንድም ቆራጥ በመሃከላችሁ የለም ! <<ፈሳም ሁላ !! >> << ወያኔ እንዳንቺ አማሪካን ሀገር በርገር እየበላች መሰለሽ ስልጣን ላይ የወጣችው ? ታግላ ነው ፣ ከገባሽ >> ደሞ እኛ ልማት ላይ ነን ! አንቺን የሚያስጨንቅሽ ያንድ ጋዜጠኛ መሞት ነው አይደል ? እኛን የሚያስጨንቀን ግን ያርማታ ሙሌት ነው ? አንቺ እስክንድር ለምን ታሰረ የሚለው ነው አይደል እንቅልፍ የሚነሳሽ ? እኛን ወያኔዎችን እንቅልፍ የሚነሳን የሲሚንቶው መቡካት ወይም አለመቡካት ነው ፣ እኛን የሚያስጨንቀን የአበባ እርሻው ነው ፣ እኛን የሚያስጨንቀን የኦባማ በሰላም ወጥቶ መግባት ነው ፣ እኛ የልማት ኃይሎች ነን ። አሁን አንድ አቡበከር ተፈታ አልተፈታ ለኢትዮጵያ ምን ይጠቅማታል ? ከገባሽ እኛን የሚያስጨንቀን እንዴት ለቀጣዩ 100 ዓመት ያለ ተቀናቃኝ እንደምንገዛሽ ነው ።

አሁን እስኪ ማን ይሙት ወያኔን የመሰለ ስርዓት በኢትዮጵያ ምድር ተፈጥሮ ያውቃል? አንድ ዘር ፣ አንድ ዘር የምትሉት ደሞ ትግሬ ስለምትጠሉ ነው እንጂ ፣ ትግሬ ቢገዛ ምን አለበት ? ትግሬ ምን አረገ ? እኛ ከዘረኛ አማራ አድነናችሁ ፣ ትግሬ ፣ ትግሬ ትላላችሁ ? ደሞ ስልጣኑ አይ ማን ነው ያለው ? ሃይለማርያም ትግሬ ነው ? ነጋሶ ገዳዳ ትግሬ ነበር ? ግርማ ወልደጊዮርጊስ ትግሬ ነው ? ደመቀ መኮንን ትግሬ ነው ? አንድ ትግሬ ስልጣን ላይ የነበረ መለስ ብቻ ነበር ፣፣ እሱም በጭንቅላቱ ነው ፣ አሁን ደሞ እሱ ሞተላችሁ ( ሞቶም አልተዋችሁትም እንጂ !) ፣ ሃይለማርያም ጠቃላይ ሚኒስትር ሲሆን ደሞ ምን እንደምትሉ እናያለን ዘረኞች ! ስለ ጀነራሎች የምታወሩት ደሞ እኮ ፣ እነሱ ታግለው ነው ፣ ለ 17 ዓመት አፈር በልተው ፣ ታዲያ አንድ ባለ እስክርቢቶ አማራ መጥቶ ይውሰደው ? ደርግ ይምጣ እና ይግዛን ነው የምትሉት ? ይልቅ አንዳንድ ጥቃቅን ስህተቶች ይኖራሉ ፣ እነሱም በሂደት የሚስተካከሉ ናቸው ። እኛ በዲሞክራሲ ስርዓት ላይ መጏዝ ከጀመርን ገና 25 አመታችን ነው ። ዲሞክራሲ ምን እንደነበር ለማያውቅ ሕዝብ ፣ ሁሉንም ባንዴ ብንፈቅድለት ቀስ እያልን እናድርገው ብለን ነው ፣ ደሞ እናንተስ እንኳን የኛን ዲሞክራሲ ፣ የባቄላ ፈስ በቅጡ መቆጣጠር የሚችል መቀመጫ ሳይኖራችሁ ዘላችሁ ወንበር ላይ ቁብ ማለት ምን የሚሉት ችኮላ ነው ።

አንዳንድ ሽብርተኞች ፣ ህገ መንግስቱን ለመናድ ከውጭ ኃይሎች እና ሰርጎ ገቦች ጋ በማበር ፣ ድርጅታችን ኢህአዲግ ቀን ከሌት ፣ ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይል እየተጋበት ያለውን የወደ ልማት ጎዳና ባጭር ለመቅጨት ቢሞክሩም ፣ የድርጅታችንን አላማ በተረዱና ፣ በድርጅታችን ላይ ላለፉት ሃያ አመታት ትልቅ እምነት በጣሉ ግለሰቦች ( በግል ተነሳሽነት ) ይህ የወንጀል ተግባር በቁጥጥር ስር ሊውል ችሏል ። ከዚህም ውስጥ እንደምሳሌ የዚህ የሽብር ቡድኑ መሪ እና ዋነኛ ተዋናይ የነበረውን ሰው ( አንዳርጋቸው ጽጌ ) በቁጥጥር ስር አውለናል ። ያም ቢሆን ድርጅታችን ፣ አንዳርጋቸው ለመጽሐፍ ያለው ፍቅር ፣ የኛን የባለ ራዓዩን ጠቅላይ ሚንስትር ፍቅር ስላስታወሰን ፣ በራሳችን ተነሳሽነት ፣ ሙሉ ወጪውን ሸፍነን << አንዳርጋቸው ሆይ ኤርትራ ውስጥ ቦምብ ከምታፈነዳ ፣ እዚህ እኛ ጋ መጽሐፍ አሳትም >> ብለነው ፣ እሱም ምክራችንን ተቀብሎ መጽሐፍ እየጻፈ ነው ። ካላመናችሁ ጠይቁት ፣ እንደውም ዛሬ ገጽ 180ን ጽፎ ጨረሰ ! እንዴትም ብሎ ለጉምቦት ሃያ አለበለዚያ ለባዕለ የካቲት ወይም ፓርላማ ተመርቆ ከመከፈቱ አንድ ሳምንት በፊት ለአንባብያን እንደሚደርስ በዚህ አጋጣሚ መግልጽ እንፈልጋለን ።

እና አባካችሁ ፣ ይህን ” ደሙን ሰጥቶ፣ አጥንቱን ከስክሶ ፣ የስኬት ማማ ላይ ያስቀመጣችሁ ጀግና ስርዓት አትፈታተኑት ! አረ ተው ታማኝ ተመከር ! አሁን ወያኔን አሜን ብለህ ብትቀበል እኮ፣ እንደ ንዋይ ደበበ ጥሬ ስጋ ስትበላ ፎቶ ተነስተህ ትለጥፍ ነበር ፣ ደደቢት ታንክ ላይ ሆነህ ፎቶ ትነሳ ነበር ፣ ከፈለካት አይነት ሴት ጋ እንደፍለክ ትሆን ነበር ፣ አንተ ግን ዝም ብለህ ነጻነት ፣ እኩልነት ፣ የህዝቦች መብት እና ወዘተ ትላለህ ። ህዝቡ ራሱ ( በብላሽ !) ፣ በኪሳራ ነው ኑሮውን ለባርነት ፣ ህይወቱን ለጭቆኛ አሳልፎ የሰጠው ። ታዲያ አንተ ምን አገባህ ! ? ይልቅ እንደ ሰለሞን ተካልኝ ፣ ለጥሬ ስጋ ስትል ሀገርህ ላይ ፣ ለቀይ ወጥ ስትል ሕዝብህ ላይ ፣ ለሆድህ ስትል እውነትህ ላይ ተገልብጠህ ፣ የቀበሌ ስብሰባ መጥሪያ ” ሃሎ- ሃሎ ” ይዘህ ” ትናንት አንድ በሉ ፣ እሪ በል ቦሌ እሪ በል ፒያሳ ” ባልክበት ጉሮርሮህ ” ቅንድቡ ፣ እጁ ፣ አይኑ ፣ አፍንጫው” እያልክ ብትዘፍን አይሻልም ? አረ ተው ታማኝ ! አረ ተው !

አሁን አበበ ገላው ታላቁ መሪያችን ላይ ፣ ሊያውም በዓለም አደባባይ ፣ ትላልቅ ሰዎች በተገኙበት ፣ እንደዚያ መጮህ ነበረበት ? ማን ተዋረደ ? አበበብ ራሱ ! ያንን የሚያህል አስተዋይ መሪ ያዋረደ መስሎት ፣ ተሳስቷል !

አና አሁንም እኛ ልማት ላይ ነን
ከሰው ሕይወት የድንጋይ ቁመት የማረከን
እኛ አለታውያን
እኛ ኮንክርታውያን
እኛ ድልድያውያን
ከሀገር ውርደት የኛ ሆድ የበለጠብን
ከህዝብ ክብር ፣ ንዋይ እንደ ኩይሳ የደም ሲሳይ የጫነብን
ከነጻነት እና ፍቅር ፣ ጥላቻ መንገድ የሰራብን
የጥፋት ልማተኞች
የክፋት መንገደኞች
በሰው ደም የሰከርን
በአልኮል የሰከርን
በጥላቻ የሰከርን
ይህንንም በ 100 % ምርጫ ውጤት ያስመሰከርን
አስክሬኖች ነን
እና ታዲያ ምን አረግን ?

ተው ፣ አረ ተው ፣ ይህንን ” ደሙን ሰጥቶ፣ አጥንቱን ከስክሶ ፣ የስኬት ማማ ላይ ያስቀመጣችሁ ጀግና ስርዓት አትፈታተኑት !

የአስመራ ሰዎች በአዲስ አበባ – (ዜና ትንታኔ)

$
0
0

Eritreans in Addis Ababa protest against their government (Video)
ቻላቸው ታደሰ ለዋዜማ ራድዮ እንደዘገበው:

ኤርትራ በ1990 ዓ.ም ኢትዮጵያን በወረረች ማግስት መንግስት በረፊረንደሙ የተሳተፉና ለብሄራዊ ደህንነት አደገኛ ናቸው ያላቸውን በሽዎች የሚቆጠሩ ኤርትራዊያን በጅምላ ከሀገር ማባረሩ ይታወሳል፡፡ ሰዎቹ ሲባረሩ ያፈሩት ሃብትና ንብረት በአግባቡ ሳያደላድሉና በህጋዊ መንገድ ለተወካዮቻቸው ሳያስተላልፉ እንደነበርም አይዘነጋም፡፡ ይህ የግብር ይውጣ እርምጃ ብዙ ዓለም ዓቀፍ ወቀሳም አስከትሎ ነበር፡፡

የሁለቱ ሀገሮች የድንበር ጦርነት ምንጭ ሳይደርቅና ዕርቀ ሰላምም ሳይወርድ ኢህአዴግ-መራሹ መንግስት ከአምስት ዓመት በፊት ባወጣው ደንብ በወረራው ወቅት የተባረሩ ኤርትራዊያን እንደገና በኢትዮጵያ ቋሚ የመኖሪያ ፍቃድ እንዲያገኙ፣ የቀድሞ ንብረታቸው ከፈለጉም ኢትዮጵያዊ ዜግነታቸው እንዲመለስላቸው ብሎም ከሀገሬው ሰው እኩል ንብረት ማፍራት እንዲችሉ ፈቅዷል፡፡ መታወቂያና የእርሻ ቦታም ሳይቀር ተስጥቷቸው ከሀገሬው ሰው ጋር ተቀላቅለው እንዲኖሩ ሁኔታዎችን አመቻችቷል፡፡ በባንክም ተቀማጭ የነበረ ገንዘባቸውም ተመልሶላቸው እንደማንኛውም የውጭ ዜጋ በኢንቨስትመንት ዘርፍ እንዲሳተፉ፣ የማህበራዊ ግልጋሎቶችን ደግሞ ከዜጎች ጋር በእኩል እንዲያገኙ አድረጓል፡፡ ስለሆነም የዚህ ፖሊሲ መነሻና ግብ ምንድን ነው? ፖሊሲውስ በኢኮኖሚ በተዳከመችውና ወታደራዊና ፖለቲካዊ ጡንቻዋ በተመናመነባት ኤርትራ ላይ ምን ዓይነት የፖለቲካ፣ ፀጥታና ኢኮኖሚያዊ አንድምታዎች ይኖረው ይሆን? የሚሉትን ጥያቄዎች መመርመር ተገቢ ነው፡፡

በእርግጥ የኢትዮጵያ መንግስት በኤርትራዊያኑ ስደተኞች ላይ ፖሊሲውን ማስተካከል ያስፈለገው የሁለቱ ወንድማማች ህዝቦችን ለማቀራረብና ግንኙነታቸውንም ለማደስ አስቦ እንደሆነ ይናገራል፡፡ ሆኖም ግን ይህ የኢትዮጵያ መንግስት ፖሊሲ ከሰብዓዊነትና ወንድማማችነት መርሆዎች ባሻገር ሌላ ዓላማ እንዳለው መታዘብ አይከብድም፡፡

መንግስት ለበርካታ ኤርትራዊያን ስደተኛ ወጣቶችም የከፍተኛ ትምህርት ስኮላርሽፕ በመስጠት በተለያዩ የሀገሪቱ ዩኒቨርስቲዎች ተመዝግበው በነፃ እንዲማሩ እያደረገ ነው፡፡ የተማሪዎቹን ጉዳይ ምፀታዊ የሚያደርገው ግን ከጦርነቱ መቀስቀስ በፊትም በርካታ ኤርትራዊያን በሀገራችን ነፃ ትምህርት ዕድል ተሰጥቷቸው ይማሩ የነበረ መሆኑ ነው፡፡ መንግስትም ከዜጎቹ በላይ ለኤርትራዊያኑ ተማሪዎቹ ደህንነትና ምቾት አብዝቶ ይጨነቅ እንደነበር የዚህ ሪፖርት አዘጋጅ ሳይቀር በኣካል ያየው ሃቅ ነበር፡፡ ሆኖም ተማሪዎቹ በወረራው ማግስት ትምህርታቸውን ሳይጨርሱ ከሀገር ከመባረር አልዳኑም፡፡

ኤርትራዊያን ወደ ኢትዮጵያ በጅምላ መሰደዳቸው የኢትዮጵያን መንግስት ያስደሰተ ይመስላል፡፡ መጠኑ ይለያያል እንጂ መንግስት የሚከተለው ፖሊሲ ቱርክ በሶሪያዊያን ስደተኞች ላይ ከምትከተለው ጋር ይመሳሰላል፡፡ የኤርትራው መንግስትም ጅምላ ስደቱ ሀገሪቱን በሰው ሃይሏ በተለይም በወጣቶች የማራቆት (emptying the nation) ፀረ-ኤርትራ ሴራ መሆኑን ይናገራል፡፡ በእርግጥም ላለፉት አስራ አምስት ዓመታት በርካታ ኤርትራዊያን ከሀገር ተሰደዋል፡፡ መንግሰት የሚተገብረው ፖሊሲም ስደተኞችን በጣም ተጠቃሚ የሚያደርግ በመሆኑ በየቀኑ ከ70 ያለነሱ ስደተኞች ድንበሩን እያቋረጡ ይገባሉ፡፡ ሀገራችንም በአሁኑ ጊዜ ከ93 ሽህ በላይ ኤርትራዊያን ስደተኞችን እያስተናገደች ትገኛለች፡፡ ከሶሪያዊያን ቀጥለው በአውሮፓ በብዛት ሁለተኛዎቹ ኤርትራዊያን ስደተኞች እንደሆኑም የዓለም ዓቀፍ ስደተኞች ድርጅት መረጃዎች ያሳያሉ፡፡ ስለሆነም የኢትዮጵያ መንግስት ፖሊሲ ግቦች የኤርትራን ወታደራዊ አቅም ማዳከም፣ ከውጭ የሚገባው የገንዘብ መጠን በዜጎች ስደት ሳቢያ እንዲመናመን ማድረግ፣ ኢኮኖሚዋም እንዲዳከምና ውስጣዊ ተቃውሞ እንዲቀሰቀስ ማድረግ እንደሆነ ይገመታል፡፡

ይህ የተናጥል ፖሊሲ ግን ምን ያህል ውጤታማና አዋጭ ነው? በኤርትራ ላይስ ምን ዓይነት ተጨባጭ ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ የፀጥታና ማህበራዊ አንድምታዎች ይኖሩት ይሆን? የሚሉት ጥያቄዎች መነሳት ያለባቸው ናቸው፡፡ በንብረት ጉዳይ ላይ ተወሰነው ውሳኔ ሀገራችንን ብዙ ዋጋ ማስከፈላቸው አይቀርም፡፡

ለዚህም ተጠያቂ የሚሆነው የቀድሞው የመንግስት ዝርክርክና የተቻኮለ አሰራር ይሆናል፡፡ ፖሊሲው ወደፊት የሚያመጣው የደህንነት ስጋት ካለም ወደፊት የሚታይ ይሆናል፡፡ መንግስት ግን ወደ መሃል ሀገር የሚገቡት ኤርትራዊያንና የደንቡ ተጠቃሚ የሚሆኑት የደህንነት ስጋት የማይፈጥሩ መሆናቸው ተረጋግጦ እንደሆነ ይናገራል፡፡ ሆኖም ግን በሚስጥራዊነቷና በመገለሏ “አፍሪካዊቷ ሰሜን ኮሪያ” በምትባለው ኤርትራ ውስጥ ሃቁን በምን መልኩ እያጣራው እንደሆነ ለማወቅ አዳጋች ነው፡፡

ስደቱ የኤርትራን መንግስት ፖለቲካዊ ዋጋ ቢያስከፍለውም የኢትዮጵያ መንግስት ፖሊሲ ግን ምን ያህል የኤርትራዊያንን ልብ ማሸፈት ይችላል የሚለው ወደፊት የሚታይ ቢሆንም ከድሮም እጁ አመድ አፋሽ የሆነው መንግስት ወጥነትና ግልፅነት ከጎደለው ፖሊሲው እምብዛም ትርፍ ያገኛል ብሎ ማሰብ አዳጋች ነው፡፡

ከኤርትራ በኩል ሲታይ ደግሞ በእርግጥ በርካታ ዜጎች በፈለሱ ቁጥር ከውጭ በሪሚታንስ (remittance) መልክ የሚገባው የገንዘብ መጠንም መቀነሱ አይቀርም፡፡ ይህ ደግሞ በውጭ ምንዛሬ ላይ ለሚተማመነው መንግስት የራስ ምታት ይሆንበታል፡፡ የኢትዮጵያ መንግስትም ለዚህ ነው ባላንጣውን በቀጥተኛ ወታደራዊ ጥቃት ከመምታት ይልቅ በኢኮኖሚ ማዳከም የመረጠው፡፡ የኤርትራ መንግስት በገጠመው የምንዛሬ እጥረት ምክንያት ካናዳና እንግሊዝን ጨምሮ በተለያዩ ሀገሮች የሚገኙ ኤርትራዊያን የሁለት በመቶ አስገዳጅ ህገ ወጥ “ዲያስፖራ ታክስ” (diaspora tax) እንዲከፍሉ በማድረጉ ከመንግስታቶቹ ጋር ዲፕሎማሲያዊ ውዝግብ ውስጥ መግባቱ በተደጋጋሚ በሜዲያ መዘገቡ ይታወሳል፡፡ ስለሆነም አሁን በኢትዮጵያ የሚኖሩ ስደተኞችም በውድም በግድም የዚሁ ግዴታ ሰለባ ላለመሆናቸው ዋስትና የለም፡፡

ሀገሪቱ ከህዝብ ብዛቷ አንፃር ሲታይ በከፍተኛ ደረጃ ሕዝቧን ያስታጠቀችና ወታደራዊ ስልጠና የሰጠች (militarised state) እንደሆነች ይታወቃል፡፡ ሆኖም ከኢትዮ-ኤርትራ ጦርነት ቀደም ብሎ ስለ ግዙፍነቱ ይነገርለት ከነበረው የኤርትራ ጦር ሃይልም ባለፉት ጥቂት ዓመታት በርካታ ወታደሮች እየከዱ ወደ ኢትዮጵያና ሱዳን መሻገራቸው በእርግጥም የሀገሪቱን ወታደራዊ አቅም ከማዳከምም አልፎ ደህንነቷንም አደጋ ላይ ሊጥል ይችላል፡፡

በዚህም ምክንያት ሳይሆን አይቀርም ከሶስት ዓመት በፊት ከኢትዮጵያ ጦር ሰራዊት ድንበር ዘለል ወታደራዊ ጥቃት ሲፈፀምበት ጦር ሰራዊቷ ምላሽ መስጠት ያልቻለው፡፡ አሁን ባለበት ሁኔታም ከኢትዮጵያ ጋር ፊት ለፊት ጦርነት የመግጠም እድሉ አናሳ ነው፡፡ የመንግስት ፖሊሲ ከሀገር የሚሸሹትን ባሉበት እንዲገደሉ የሚያዝ ቢሆንም የጦር ሰራዊቱ አመራሮች ግን በሰው በሽዎች የሚቆጠር ናቅፋ እየተቀበሉ ስደተኞችን ወደ ጎረቤት ሃገር በማሻገሩ ወንጀል እንደተዘፈቁ ዓለም ዓቀፉ የግጭት ጥናት ተቋም (International Crisis Group) ይገልፃል፡፡ በዚህ ሁኔታ ውሎ አድሮ ጦር ሰራዊቱም ሞራሉ እየላሸቀ ስለሚሄድ በጣሙን የመዳከም አደጋ አንዣቦበታል ማለት ይቻላል፡፡

አዲስ አበባ ያሉት የአቶ የአቶ ኢሳያስ አፈወርቂ መንግስት ተቃዋሚዎች ትጥቅ ትግል ስለማያደርጉ ኤርትራዊያን ስደተኞቹን የማደራጀትና የመመልመል ስራ አይሰሩም፡፡ በእርግጥ ኤርትራ የኢትዮጵያን መንግስት በነፍጥ የሚፋለሙ ሓይሎችን ብትደግፍም ኢህአዴግ-መራሹ መንግስት ግን ተመሳሳይ ፍላጎት ያለው አይመስልም፡፡ መንግስት ይህንን የማያደርገው ግን በኤርትራ ላይ ከሚከተለው ዋናው ፖሊሲ ጋር የሚጋጭበት ስለሆነ አይደለም፡፡ ምን ያህሎቹ ኤርትራዊያን ስደተኞች መንግስታቸው በሃይል እንዲወገድ ይፈልጋሉ? የሚለው ራሱ አጠያያቂ ነው፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ የኤርትራ መንግስት በሃይል ቢገረሰስ ሀገሪቱን ሊረከብ የሚችል አስተማማኝ አማራጭ ሃይል እንደሌለም የኢትዮጵያ ባለስልጣናት ጠንቅቀው ያውቃሉ፡፡

በያዝነው የፈረንጆች ዓመት ኤርትራዊያን በመንግስታቸው ላይ የተቃውሞ ሰልፍ ከማድረጋቸው ውጭ ኤርትራዊያን ስደተኞች የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች በተባበረ መንገድ በዓለም ዓቀፍ ደረጃ ለማጋለጥ ሲጥሩ አይታዩም፡፡ ምናልባት ሀገር ውስጥ ላሉ ቤተሰቦቻቸው ደህንነት ስለሚሰጉ ይሆናል፡፡

በጦር ሰራዊቱ ውስጥም ቢሆን ከሶስት ዓመታት በፊት አስመራ ላይ ከታየው የጥቂት ወታደሮች የአጭር ጊዜ መጠነኛ አመፅጥ (mutiny) በስተቀር ምንም የአመፅ እንቅስቃሴ አይስተዋልም፡፡ በዚህ ረገድ የኢትዮጵያ መንግስት በኤርትራ ላይ ያገኘው ፖለቲካዊ ድል የለም ማለት ይቻላል፡፡

ኤርትራዊያን በብዛት የሚገኙባቸው አፍሪካዊያን ስደተኞች ሜዲትራኒያን ባህርን እያቋረጡ በብዛት ወደ በአውሮፓ ከመግባታቸው ጋር በተያያዘ ኤርትራ በቅርቡ መልካም ዜና ሰምታለች፡፡ የአውሮፓ ህብረት የኤርትራ መንግስት ፍልሰቱን እንዲቀንስ 313 ሚሊዮን ዩሮ የገንዘብ እርዳታ ሊለግስ ቃል ገብቷል፡፡

በእርግጥ የህብረቱ ውሳኔ ተግባራዊ ከሆነ በኢትዮጵያ መንግስት ፖሊሲ ላይ በረዶ የሚቸልስ ይሆናል፡፡ በአንፃሩ በውጭ ምንዛሬ እጥረት ለሚሰቃየው የኤርትራ መንግስት ደግሞ ከሰማይ የወረደ መና እንደሚሆንለት አይካድም፡፡

የኤርትራ መንግስትና ሰራዊት ዋነኛ ኢኮኖሚያዊ ዋልታ የሆነውን የማዕድን ዘርፍ ሊያነቃቃው እንደሚችል ታዛቢዎች ይገምታሉ፡፡ ይህ ተግባራዊ ከሆነ በሂደትም በመንግስቱ ላይ የተጣሉ አንዳንድ ማዕቀቦች ሊነሱም ይችላሉ፡፡ ይህንን ሚስጢራዊ የተባለ ስምምነት ለመተግበርም የተለያዩ የህብረቱ ባለስልጣናት ኤርትራን ሲጎበኙ ሰንብተዋል፡፡

ይህ እንግዲህ አውሮፓ ህብረት የስደቱ ዋነኛ መንስዔ ኢኮኖሚያዊ ነው ብሎ ማመኑን ያሳያል፡፡ ውሳኔውን ተከትሎም እንግሊዝ ለኤርትራዊያን ስደተኞች ጥገኝነት መስጠት የቀነሰች ሲሆን ህገወጥ ኤርትራዊያን ስደተኞችንም ከሃገሯ ለማስወጣት በመዛት ላይ ስለመሆኗ የእንግሊዙ “ዘ ጋርዲያን” ጋዜጣ በቅርቡ ዘግቦ ነበር፡፡ የህብረቱ ውሳኔ ግን ከተባበሩት መንግስታትና ዓለም ዓቀፍ ሰብዓዊ መብት ድርጅቶች ተቃውሞ እየገጠመው ይገኛል፡፡ በሀገሪቱ ያለውን ኢኮኖሚያዊ ችግር መካድ ባይቻልም ስደቱ በመብት ጥሰት ሳቢያ የመጣ መሆኑን ዓለም ዓቀፍ ሰብዓዊ መብት ድርጅቶች ይገልፃሉ፡፡ በቅርቡም የተባበሩት መንግስታት ሰብዓዊ መብት አጣሪ ኮሚቴ የኤርትራን መንግስት በአስከፊ ሰብዓዊ መብት ጥሰቶች ክፉኛ መከስሱ ይታወሳል፡፡

በሀገሪቱ ውስጥ ያሉ ነባራዊ ሁኔታዎች እንደተጠበቁ ሆነው በጥቅሉ ሲታይ ግን የኢትዮጵያ መንግስት ፖሊሲ በኢሳያስ መንግስት ላይ ጠንካራ ፖለቲካዊ ንቃቃትን መፍጠር አልቻለም፡፡

ታዛቢዎችም በኤርትራ በኩል ተመሳሳይ አወንታዊ እርመጃ ሳይኖር የኢትዮጵያ መንግስት የተናጥል እርምጃ መውሰዱ የኢትዮጵያን ህዝብ ጥቅም አያስጠብቅም በማለት ይተቻሉ፡፡ አሁንም ቢሆን ስደተኞችን መንከባከብ ተገቢ መሆኑ እንደተጠበቀ ሆኖ የመንግስት አካሄድ በድምሩ ሲታይ ግን ከወረራው በፊት የነበረውን ሁኔታ በሙሉ ወደነበረበት ለመመለስ የሚፈልግ አስመስሎበታል፡፡ በእርግጥም የፖሊሲው ዓላማ በህዝቦች ወንድማማችነት ሽፋን በኤርትራው መንግስት ላይ የበቀል እርምጃ መውስድ ዋነኛ ታሳቢው ያደረገ ነው ማለት ይቻላል፡፡

«ፅናት እና እውነታው»

$
0
0

news ethiopia 2
ከአቡ ሙስአብ
ለኢንጅነር መሃመድ አባስ

ሰሞኑን በተለያዩ ማህበራዊ ድህረ ገፆች እዬተናፈሰ ያለውን ወሬ ለጎልጉል እንዲሁም ለዘ ሃበሻ ኔት የተሳሳተ መረጃ ያቀበሉት ኢንጅነሩ ቢሆኑም እንደ ሚዲያ መጀመሪያ ፅሁፉን ከመለጠፍ በፊት ይመለከተዋል የተባለውን አካል አነጋግሮ እውነታውን ማጣራት ተገቢ ነበር:: ሆኖም ያሳሆን በችኮላም ይሁን በግድዬለሽነት ፅሁፉ ተለጥፎ በአንዳንድ ሙስሊም ወገኖች ዘንድ ብዥታን የፈጠረ ሲሆን እውነታው ግን ከዚህ በፍፁም የተለዬ መሆኑ ለኢንጅነሩ ምናልባት ያልተረዱት እውነታ ወይም ግላዊ ጥላቻ ካላቸው ስለ «ፅናት» የማውቀውን እውነታ ለማቅረብ እሞክራለሁ።

ፅናት የኢትዮጵያ ሙስሊሞች ማህበር በሂጅራ አቆጣጠር 16/3/1435 የዛሬ አመት ከመንፈቅ አካባቢ የተመሰረተ ሲሆን

መስራቾቹም በሃገራችን ሙስሊሞችላይ መንግስት እዬወሰደ ካለው መራር ግፍና መከራ ግንባር ቀደም ገፈት ቀማሽ የሆኑ በሃገራቸው በተለያዩ የዲን ዘርፍ አንቱታን ያተረፉ የብዙሃን ሂወቶችን ወደቀጥተኛው ጎዳና ወደ ኢስላም በአላህ ፈቃድ የለወጡ ታላላቅ ኡለማዎች ናቸው እንግዲህ እንደ ኢንጅነሩ ሃሳብ እነዚህ በችግሩ ምክንያት በሃገራቸው መብታቸው ተነፍጎ መኖር ስላልቻሉ ከሚወዱት ህዝብና ቤተሰቦቻቸው ተለይተው በተለያዩ ሃገራቶች በስደት የሚኖሩ ኡለማዎችን ከበሬ ወለደ ግላዊ ጥላቻቸው በመነሳት ቀጥታ ከህዋሃት ስውር ሴራ ጋር እነሱን ማያያዛቸውና መፈረጃቸው ምናልባት እንደሙስሊምነታችን እንድ ነገር ወደኛ በመጣ ጊዜ የነገሩን እውነታ ሳናጣራ በስሜት ተነሳስቶ መፈረጁ የታላቁን ቁርአን ህግ በመጣስ በሰዎቹ ላይ የውሸት ውንጀላ ማቅረቡ ከባድ ስህተት መሆኑን ቢረዱት መልካም ነው ።

እንግዲህ እነዚህ ብርቅዬ ኡለማዎቻችን ከሃገር ተሰደውም ቢሆን በሃገራቸው ሙስሊም ማህበረሰብ ላይ የሚደርሰውን ግፍና መከራ ስለሚያሳስባቸውና ስለሚያስጨንቃቸው «ፅናትን»ለመመስረት በቁ አላማቸውም እንደ ማለዳ ጮራ ፍንትው ያለ ምንም ብዥታ የሌለበት ነው ይኼውም በኢትዮጵያ ሙስሊም ማህበረሰብ ላይ የሚደርሰውን ግፍና በደል በሁለንተናዊ መልኩ ችግሩን መካፈል ማለትም በዚህ ችግር ሳቢያ የተዘጉ መድረሳዎችን አገልግሎት እንዲሰጡ የተለያዩ ኡለማዎችን የወር ደመዛቸውን በመክፈል በተለይም ታዳጊ ህፃናት የቁርአንን ብርሃን አግኝተው እነሱም ያንፀባርቁ ዘንድ እስካሁን ድረስ በተለያዩ አካባቢዎች ይህ ነው የማይባል ያላሰለሰ ጥረት እያደረጉ ይገኛሉ

በተጨማሪም በትግሉ ምክንያት በተለያዬ ምክንያተ ችግር ላይ የወደቁ ወንድሞችን እና እህቶችን በተለይም የጠበቃ መክፈል ሳይችሉ ቀርተው በሃገራችን የነገሰው የፍርድ ድርቅ ምንም እንኳን ተስፋ አስቆራጭና «ከዝንብ ማር» የማይጠበቅ ቢሆንም ለነዚህ በተለያዩ ሃገራት እስርቤት ለሚሰቃዩ ታጋዮች የጠበቃ እና የቤተሰቦቻቸውን በመሸፈን የተለያዩ እገዛዎችን እያደረጉ ይገኛሉ ።

ሌላው ኢንጅነሩ የተሳሳቱት መረጃ ቢኖር እንዳሳቸው አባባል «በሳውዲ አረቢያ በሚኖሩ ሴት እህቶቻችንን በማሳሳት ገቢያቸውን ያደልባሉ» ኢንጅነር ሆይ እንደርሰዎ ጭፍን ጥላቻ ሳይሆን የፅናት የገቢ ምንጭ ከመላው አለም የሚገኙትን ከማህበሩ አባላት ከወንዱም ከሴቶች እህቶቻችንንም በየወሩ ከሚሰበሰብ አነስተኛ የአባላት መዋጮና እንደዬ አባሉ በጎ ፍቃድ በሚነዬቱ (በሚለገሱ) ገቢዎች ከላይ የጠቀስኳቸወወን እና ሌሎች መሰል በጎ ተግባራቶችን በመስራት ትግሉን በሚችሉት መልኩ እዬደገፉ ይገኛሉ ።

ኢንጅነሩ ከመረጃ የራቁና ስለፅናት ያላቸውን ጥላቻ ያሳዩበት ሌላው ስህተት ደግሞ በውድና ጀግና ኮሚቴዎቻችን የተፃፉ መፅሃፎችን ማለትም የኡስታዝ ያሲን ኑሩን «ግብህን ቅረፅ »እና የታሪክ ሙሁሩን አህመዲን ጀበል«ፈርኦን የአምባገነኖች ተምሳሌት» የተሰኙትን መፅሃፍ በማሳተም ገቢውን ወደኪሳቸው አስገብተዋል ሲሉ ምንም መሰረት የሌለው ካባድ ስህተት ተስተው አሳስተዋል እውነታው ግን «ፅናት የሙስሊሞች ማህበር» ከ«ድምፃችን ይሰማ» ጋር በመተባበር «ድምፃችን ይሰማ በሳውዲ አረቢያ» ያሳተማቸውን መፅሃፎች የታሪክ ሙሁሩ አህመዲን ጀበል «ኒፋቅና የሙናፊቆች ማንነት ሲጋለጥ» እንዲሁም «በድምፃችን ይሰማ»የተዘጋጀውን «የተዘነበለ ፍትህ» የተሰኙትን መፅሃፍት ከምርቃቱ ጀምሮ መፅሃፍቶቹን ለአባላቱ በማስተዋወቅ እና በማሻሻጥ እንዲሁም «ድምፃችን ይሰማ በሳውዲ አረቢያ»በሚያወጣቸው የተለያዩ ፕሮግራሞች ላይ በመገኘት አጋርነቱን በተግባር ቢያረጋግጥም ኢንጅነሩ ግን መሰረት የሌለው የሐሰት ውንጀላቸውን ጭራሽ ይባስ ብለው «ድምፃችን ይሰማ በሳውዲ አረቢያን» ለመንግስት ለማጋለጥ ሲሰሩ ነበር ሲሉ ኮንነዋል። «ፅናት»በመነጋገር በመወያዬት ክፍተት ሊያመጡ የሚችሉ ጉዳዮችን በመተው በአንድነትና በወንድማማችነት በጋራ ወደምንጓጓለት የድል ምእራፍ ተሸጋግሮ ህዝበ ሙስሊሙ በሰላም በገዛ ሃገሩ በነፃነት እምነቱን ይተገብር ዘንድ ለሚተላለፉት የሰላማዊ ትግል ስልቶች ግንባ ቀደም ተሰላፊ በመሆን
«ከድምፃችን ይሰማ በሳውዲ አረቢያ»ጋር ያለውን ግንኙነት የበለጠ ማጠናከሩን ያሳያል።

እንግዲህ ኢንጅነሩ ከላይ የጠቀሱዋቸውን መፅሃፍት በፅናት ታትመል ሲሉ ነጭ ውሸትን ዋሽተዋል
ሌላውና ትልቁ ጉዳይ« ፅናት» «በድምፃችን ይሰማ » አመራር ላይ እንቅፋት ፈጥረዋል ብለው የወነጀሉት ሲሆን« ፅናት የሙስሊሞች ማህበር»እንደ ዋና ተግባር ከያዛቸው ስራዎቹ አንዱ ለድምፃችን ይሰማ ታዛዥ መሆኑን እና በሚወጡ የትግል መርሃዊ ግብሮችላይ በንቃት በመሳተፍ መተግበር መሆኑ እስካሁን ድረስ እያረጋገጠው ያለ እውነታ ነው ።

በመጨረሻም በተደጋጋሚ ብዙ የዋትሳፕ ግሩፖችን ከፍተው ሙስሊሙን ይበዘብዛሉ እያሉ ኢንጅነሩ ሲወቅሱ ነበር እውነታውግን በተለያዩ የዋትሳፕ ግሩፖች የተሰባሰቡ አባላቶችን በተለያዩ የማህበሩ መስራች ኡለማዎች አማካኝነት የአባላትን እውቀት ከፍ ሊያደርግ የሚችሉ የዲን ትምህርቶችን ማለትም
ተውሂድ
ፊቂህ
ተፍሲር
ሲራ
ብሉግ እና ሌሎችም መሰል የዲን ትምህርቶቹን በቀላሉ ለሙስሊሙ ኡማና ለአባላቶቹ በዋትስአፕ በማዳረስ ከማያልቀው የእውቀት ማእድ በማቋደስ ትውልድን በመነፅ ላይ ይገኛል ።
እንግዲህ ውድ አንባቢያን ስለፅናት የማውቀው ትክክለኛ እውነታ ይሄ ነው ምናልባት ኢንጅነሩ ደርሷቸው እውነታውን ሲረዱ የማስተካከያ ፅሁፍ እንደሚሰጡን ተስፋ አደርጋለሁ
ድል ፍትህ ለተጠማው ኡማ !!!


በወሎ በዝናብ እጥረት አዝመራ እየደረቀ ነው ተባለ * በአፋር በድርቁ የተነሳ በቀን ከ100 በላይ ከብቶች እየሞቱ ነው

$
0
0

Zehabesha News
afar
ዘ-ሐበሻ ከሰሞኑ ጀምሮ በአፋር ክልል ድርቅ እየተከሰተ መሆኑን; ዝናብም ከጣለ አንድ ዓመት እንደሞላው በተለይም ከብቶች እየሞቱ መሆኑን መዘገቧ አይዘነጋም:: ከወሎ አካባቢ ለዘ-ሐበሻ በድረሰው መረጃም እንዲሁ ዝናብ ባለመጣሉ የተነሳ የተዘራው እህል እየደረቀ የምግብ እጥረት እያስከተለ ነው::

ከወሎ አካባቢ የሚደርሱን መረጃዎች እንደሚያመለክተው መንግስት ይህን ለማስተባበል እየሞከረ ቢሆንም ችግሩ አግጦ እየታየ ነው::

በሌላ በኩል ዛሬ በአዲስ አበባ ታትሞ የወጣው አዲስ አድማስ ጋዜጣ የሚከተለውን ዘገባ አስተላልፏል:-

ባለፉት ሁለት ወራት በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች የተከሰተው የዝናብ እጥረት የድርቅ አደጋ እንዳይከሰት ስጋት የፈጠረ ሲሆን ግብርና ሚኒስቴር በበኩሉ፤ የዝናብ እጥረት ቢኖርም የድርቅ አደጋና የምግብ እጥረት ስጋት የለም ብሏል፡፡
በአፋር ክልል ግን ሁኔታው ተባብሷል፡፡ በየቀኑ እስከ 100 የሚደርሱ ከብቶች በመኖና በውሃ እጥረት እየሞቱ መሆኑን ምንጮቻችን ጠቁመዋል፡፡
የአፋር ክልልን አቋርጠው ወደ ጅቡቲ ወደብ ከሚጓዙ ሹፌሮች አንዱ ለአዲስ አድማስ እንደገለፀው፤ በመንገድ ዳርና ዳር በርካታ በጎችና ፍየሎች ሞተው ይታያሉ፡፡
በክልሉ ካለፈው ዓመት ሰኔ ወር ጀምሮ እስካሁን ድረስ ዝናብ የጣለባቸው ቀናት በጣት የሚቆጠሩ መሆናቸውን የጠቆሙት ምንጮች፤ የድርቁ ሁኔታ እየተባባሰ ቢሆንም በመንግስት በኩል ፈጣን እርምጃ አልተወሰደም ሲሉ ቅሬታቸውን ገልጸዋል። የግብርና ሚኒስቴር ግን በዚህ አይስማማም። የዝናብ እጥረቱ የፈጠረው ድርቅ በእንሰሳቱ ላይ የከፋ ጉዳት እንዳያደርስ ከክልሉ መንግስት ጋር በመቀናጀት የመጠጥ ውሃና መኖ በማቅረብ ላይ መሆኑን ጠቁሞ ከብቶች እየሞቱ ነው ስለሚባለው ግን መረጃው እንደሌለው ገልጿል፡፡
በክልሉ የተከሰተው ድርቅ የሚያደርሰውን ጉዳት ለመከላከል አስፈላጊው ሁሉ እየተደረገ ነው ያሉት የሚኒስትሩ የኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ም/ኃላፊ አቶ ወንድሙ ፍላቴ፤ “ሀገሪቱ በቂና አስተማማኝ የአደጋ መከላከል ዝግጁነት አላት” ብለዋል፡፡
ምንጮቻችን እንደሚሉት፤ በተለይ በአማራ ክልል በወሎ እንዲሁም በሐረር አካባቢ በተከሰተው የዝናብ እጥረት የድርቅ ስጋት አንዣቧል፡፡
ዘንድሮ በአገሪቱ የሰሜንና ምስራቅ እንዲሁም መካከለኛ ክፍሎች በአየር ፀባይ ለውጥ (ኤሊኖ) የተነሳ የዝናብ እጥረት መፈጠሩን የጠቆመው ግብርና ሚኒስቴር፤ በሰኔና በሐምሌ ይጠበቅ የነበረው ዝናብ መቆራረጥ ቀድሞ የተዘሩ ሰብሎች እንዳይበቅሉ ቢያደርግም ከነሐሴ ጀምሮ መዝነብ መጀመሩንና ቀጣይነት እንደሚኖረውም ገልጿል፡፡
“ገበሬዎች ዝናብ ሲዘንብ ጠብቀው ውሃውን በማቆር ለሰብሎቻቸው እንዲጠቀሙ እየተደረገ ነው፤ የግብርና ልማት ጣቢያ ሰራተኞችም የወትሮው የግብርና ስራ እንዳይስተጓጎል ያልተቋረጠ ድጋፍ እያደረጉ ነው” ብለዋል ም/ኃላፊው፡፡
በአሁኑ ወቅት ግብርና ሚኒስቴር የዝናብ እጥረቱን መቋቋም የሚችሉ የድንች፣ ስንዴ፣ ማሽላ፣ ጤፍና የመሳሰሉ ሰብሎችን ምርጥ ዘር በማቅረብ ችግሩን ለመከላከል ጥረት እያደረገ መሆኑንም ኃላፊው ጠቁመዋል፡፡ በተለይ የሰብል አምራች በሆኑ አካባቢዎች የተከሰተው የዝናብ እጥረት በቀጣይ ዓመት የሃገሪቱ የምርት አቅም ይቀንሳል፣ ረሃብም ሊፈጠር ይችላል የሚል ስጋት እንዳላቸው ምንጮቻችን የገለፁ ሲሆን ግብርና ሚኒስቴር በበኩሉ፤ የተፈጥሮ ክስተቱ ፈታኝ ቢሆንም ሃገሪቱ በቂ የአደጋ መከላከል ዝግጁነት እንዳላት ጠቁሞ፣ በቂ ምርት ማግኘት እንደሚቻልና የምግብ እጥረት ስጋት እንደማይኖር አስታውቋል፡፡

ውድ ቴዲ አድሃኖም – ውሸትም ክብር አለው (ከስንሻው ተገኘ)

$
0
0

High-level Meeting on Disability and Development
ስንሻው ተገኘ

በምገኝበት አገር አብሮኝ የሚሰራ አፍሪካን-አሜሪካን ወዳጅ አፍርቻለሁ። ስለ ኢትዮጵያ አንዳንድ የታሪክ ግንዛቤዎች እንዲኖሩት ጉጉት ስላለው ደስ እያለኝ ከማውቃት አካፍለዋለሁ። አንዳንድ ጊዜ ግን የምደነግጠው እኔ ከማውቀው በላይ እየሄደ ስለ ኢትዮጵያ አዳዲስ ነገር፣ “ይቅርታ ምጥ ለእናቷ አስተማረች እንዳይሆንብኝ…” ይልና አዳዲስ ክስተቶችን ይነግረኛል። የትናንቱ ጥያቄው ደግሞ ልዩ ነበር። ይኸው ማይክል የምለው ጓደኛዬ “የኢትዮጵያ Gestapo ምን ስም አለው?” ብሎ አፋጠጠኝ። (በነገራችን ላይ ጌስታፖ ትልቁ የሂትለር የአፈናና የግድያ ተቋም ነበር። ይህ ከ 32,000 ሰራተኞች በላይ የነበሩት የስለላ ተቋምና ለአርያን ዝርያ ጠላት ናቸው የተባሉትን አይሁዶች፣ ኮሙኒስቶችና፣ የናዚ ፍልስፍና የሚቃወሙትን ሁሉ በስልት የሚያስወግድ ድርጅት በራሱ ጠንካራ ውስጣዊ መንግስት ነበር።)

በኢትዮጵያ የመለስን ራእይ ተከትሎ የተቋቋመ፣ ዳሩ ግን መቋቋሙ ብዙም ሳይወራ እንደ ጌስታፖ ያለ- ከቶም መብለጡን የማልጠራጠር- የስለላና የድምሰሳ ትልቅ ተቋም መፈጠሩን አልክድም። የአገራችንን የፖለቲካ ሁኔታ በቅርብና በጥልቅ የሚከታተለው አሜሪካዊ ግለሰብ ኢትዮጵያዊውን ጌስታፖ “አግአዚ ይባላል” አለኝ። ብዙ ንትርክ ለማንሳት አልፈለኩምና “አግአዚ” በአዲሱ ተቋም ውስጥ የሚገኝ ተወርዋሪ ሃይል- ጨካኝና ወደ አውሬነት የተጠጋ ስሜት ያላቸው ሰዎች ያሉት አካል መሆኑን ሳላወሳበት አልቀረሁም። የዚህ ታላቅ አካል ምርጥ የመሆኑ ምስጢር በጭካኔያቸውና በኢሰብአዊነታቸው ተመልምለው የገቡና ከጥቂት ስልጠና በኋላ ወደፍጹም “ባርባርነት” የተለወጡ ናቸው። ሂዱ ቀጥቅጡ። ከዛሬ ጀምሮ የምትጠቀሙበት ስልት በሞትና በህይወት መካከል የምታስቀሩበት፣ ጠላትን በሰውነቱ በሚያፍርበት ሁኔታ እንዲዋልል የምታደርጉበት ጥበብ ነው። …. ሌላም ሌላም ነው። ከወያኔ ገራፊዎች፣ መርማሪዎችና የህሊና ፖሊሶች እጅ ወጥተው ብዙ መናገር የሚያስጨንቃቸው ወገኖቻችን የሚነገር ብዙ ጉድ አለ።

በአንዳንድ የዚህ ሁሉ “ውርዴ” (መከራውን የጨለጡ) የሆኑ ግለሰቦች የሚዘከረው ሁሉ እስከወዲያኛው የሚቀፍፍና የሚዘገንን ነው።

በዚህ እድሜዬ ለእኔ ያንን በብዙ ወገኖቻችን ላይ የደረሰውን የወል ሩካቤ ( በሴቶችም፣ በወንዶችም)፣ በኤሌክትሪክ የመጠበስ፣ የጥፍሮች መነቀል፣ አባለዘር ማምከን፣ ህሊናን የመበረዝና፣ ልብን የመስለብ ምርመራ ወዘተ… ማውሳት አይመቸኝም። የናዚዎችን ኮንሰንትሬሽን ካምፖች ያየሁ፣ በሰብአዊነት በመረበሽ ለቀናት ስረበሽ የነበርሁትን ሁኔታ ሁሉ የማስተውል እድሜ ጠገብ ሰው ያ ወደ አገሬ ይመጣል ብዬ አስቤ አላውቅም።

እንዲህ አይነት ሰው በሰው ላይ በሚያደርሰው ጭንቀትና ስቃይ ነፍሴን እያሰቃየሁ በንባብም ጭምር መከታተሌን ሳስብ እኔም እንደ አንዳርጋቸው ጽጌ “ሞትን የመሰለ ጸጋ የት ይገኛል?” እላለሁ፥ እሱ አራዊት በማይደርሱበት “ክርስቶሳዊ ስሜት” እኔ ደግሞ እንዲህ ያለውን ፍጹም በሆነ የአራዊት አለም የሚፈጽመውን ህሊናዬ ላይ በተፈጠረው ቁስል! በነገራችን ላይ የ21ኛው ክ/ዘመን አውራ ጀግናችን የሆነው አንዳርጋቸው ጽጌ ለእንግሊዙ አምባሳደር ሞትን ማግኘት አለመቻሉን የገለጠበት ቋንቋ ብዙ መጽሃፍ ይወጣዋል። የሚናገረው ብዙ ታሪክ አለው። የብዙ ፊልም ትረካ የሚገባው ነው። ሁላችንም እንደተከታተልነው ደግሞ “የፕሮፓጋንዳ ጊኒፒግ” ሊያደርጉት በመፈለግ በቴሌቪዥን ባቀረቡት ቁጥር ስቃይን የሚመሰክሩ በሲቃ ከአፉ የሚወጡ ቃላት እስከወዲያኛው የሚዘነጉ አይሆኑም። በዚያ ባለግርማ ሰውነቱ ላይ የደረሰው መከራ፣ በህሊናው ላይ የተካሄደው አስጨናቂ አገላለጥ፣ በሁላችንም መንፈስ ላይ የጣለው ጠባሳ በቀላሉ የሚይታይ አይደለም። በተኩሱና በሌላ ሌላው ምክንያት አራዊት ከአገራችን እንደናው ተሰደው የሰው አራዊት መተካታቸው የሚገርም አይደለም። እነሆ የአራዊት ስራ!

በሌላ በኩል ደግሞ የአንዳርጋቸው የአንድ ጊዜ ኢንተርቪው የተባለው አስራ አንድ ቅጥልጥል ፊልም ግጥምጥም ነው። በሁሉም ቅጥልጥል ፊልም የስቃይ ድምፅ ተከስቷል። አንዳርጋቸው በአማርኛም ሆነ በእንግሊዝኛ ሲናገር ማንንም የሚማርክና የሚያፈዝዝ ሲሆን ራሱን እንዲያወግዝ፣ ጓደኞቹንና ሌሎችን ፀረ-ወያኔ የሆኑ ኢትዮጵያውያንን “ያለቦታውና ያለነገሩ” እንዲራገም ያስገደዱትን እንኳ በምን አይነት የመቃተት ስሜት እንደተናገረ አይተናል።

አይ ሰው የመሆን ጣጣ! እነዚህ ሁሉ ለፕሮፓጋንዳ የቀረቡ የአረመኔዎች ስራዎችና የኢትዮጵያ ህዝብ የወደቀበትን መከራ የሚመሰክሩ ናቸው። ለባረቀው ፕሮፓጋንዳ ደግሞ ለበረከት ስምዖን ልናጨበጭብ እንችላለን። (ሔኖክ የሺጥላ እንቅፋት አይምታውና “ሰሞኑን በፌስቡክ “በረከት ስምዖን ሞቶ አንዳርጋቸውን ሆኖ ተነሳ” የሚል ወደር የሌለው መጣጥፍ አቅርቦልናል። እንደእውነቱ ይበል የሚባልለት ቅኔ ነው። “ቅኔ” ሁሉ ቤት መምታት የለበትም!)

ለፕሮፓጋንዳ ብለው ባቀረቡት አንደኛው የአንዳርጋቸው መግለጫ በስተጀርባው የሚገረፍ ሰው ሃይለኛ ድምፅ ይሰማል። በቀድሞዋ ሶቪየት ህብረት ከፓርቲው መስመር ውጭ የሆነ አመለካከት ያለው ሁሉ “የሕዝብ ጠላት” የመባል ጣጣ ነበረበት። ይልቁንም በግልጽ በስነጽሁፍ ረገድ የምእራቡ አለም ያወቃቸው እንደ ሶልቬትሲን፣ ቦሪስ ፓስተርናክ፣ ሶርኮብ ወደ “ጉላጎች” እየተላኩ ምድራዊ አበሳ እንዲቀበሉ ይደረጋሉ። በኋላ ጊዜ አመለካከቱ ከፓርቲው መስመር ውጭ የሆን ሁሉ የህዝብ ጠላትነት ካባ ይደርቡለትና አዳዲስ በተቋቋሙ የሩሲያ የፖለቲካ ሆስፒታሎች እየተባሉ በሚጠሩ “ሳይካትሪካል ሆስፒታሎች” ውስጥ ይገባሉ። ገሃነም፣ ሲዖል የሚባሉ ስፍራዎች መግለጫና ማስረጃ ያገኙት በእነዚህና እንደ ሻህ ኦፍ ኢራን፣ ራሳቸው አያቱላህ ኮሚኒ፣ ኢዲ አሚን የፍርሃት ሪፑብሊክ ሳዳም ሁሴን፣ የደቡብ አፍሪካ ቮርስተር ባቋቋሙአቸው የአፈና፣ የጭንቀትና የምድራዊ ስቃይ መቀበያ ስፍራዎች ደህና መገለጫ አግኝተዋል። የወያኔ አገዛዝ ደግሞ ከኮሎኔል ጎሹ ቀደም ብለው በትንቢት መልክ እንደገለጡት ከፖልፖት ያንሰያሪ አገዛዝ የከፋ ነው።

ማጋነን አይደለም። ማጋነን አልወድምም። በእኔ በኩል እንዲያውም እውነቱን በጠንካራ ቋንቋና በውል ማስረጃ (እያለኝ) ለማብራራት አቅም ማጣት የሚሰማኝ ነኝ። ወይም በወያኔ እስር ቤቶች የደረሰባቸውን ሁሉ ለመግለጥ በባህላዊ ሽብር ውስጥ መግባት ነው። የኢትዮጵያውያን ይሉኝታና ጠበቅ ያለው ባህል የወያኔ ምርመራና እስራት ምን ማለት እንደሆነ ባለ”ውርዴዎቹ” በአደባባይ ወጥተው እንዳይናገሩ የህሊናቸው ተቆጣጣሪ አድርጓቸዋል። የአሜሪካው ዲፓትርመንት አንድ መግለጫ በተወሰኑ እህቶቻችን ላይ ወያኔዎች ያደረሱትን ወራዳ ተግባር ሲገልጥ በሚችል መልኩ “ማስረጃ አለን” ይላል። የዚያን አይነት ስቃይ የደረሰባቸው እህቶቻችን አደባባይ ወጥተው ያንን ባይገልጡ የሚፈረድባቸው አይመስለኝም። ይህ ደግሞ ወያኔዎች በባህላችን ላይ የሚጫወቱት አንድ ታሪክ ነውር መደበቂያ ሆኖላቸዋል።

ካለኝና ካላችሁ መረጃ በመነሳት ይህን “የፖሊስ ስቴት” የሆነ መንግስት ጨምላቃ ገመና መዘክዘክ ይቻላል። ይኽ ደግሞ በስሜትና በአጫጭር ሃተታ የሚጻፍ ሳይሆን ለትውልድ በሚቀሩ መጻህፍትና ፊልሞች ቢሆን ይመረጣል። በአጭሩ ለመግለጥ ግን በዛሬው ቀን በዚህ ሰዓትና ዘመን እነደብረጽዮንና ጌታቸው አሰፋ ከሚመሩት “ፖሊስ ስቴት” የባሰ ገሃነም በአለም ላይ ያለ አይመስለኝም። ( ወያኔዎች ገና የመንግስትነትን ስም ከመቀዳጀታቸው በፊት በትግራይ ህዝብ ላይ ሲያደሩ የኖሩትን ስቃይ ከሚገልጸው “አሞራ” ከተሰኘው መጽሃፍ አንስቶ እስከ ካፕተን ተሾመ ተንኮሉና፣ የዱባይ ወንድማችን መግለጫ ቪዲዮ ድረስ ያለውን ሁሉ ተከታትያለሁ። ኢትዮጵያ ከፖልፖቱ ካምቦዲያ፣ ከሳዳም ሁሴን ኢራቅ፣ ከ… የባሰች የጭንቀት አገር ናት። ጓደኛ የላትም። እንደተከታተላችሁት ደግሞ ውዱ ጠቅላይ ሚኒስትራችን በፕሬዚዳንት ኦባማ ጉብኝት “ገለጣ”ው ላይ እስካሁን የተፈጸመው ሁሉ በ “ዲሞክራሲ ልምምድ” መልክ ነበር። በሩብ አመት አላለቅንም። ሁለተኛው ሩብ ምዕተ-አመት እየቀጠለ ነው።

ከገሃነም ያመለጡ እህቶቻችን፣ ወንድሞቻችንና ጓደኞቻችን የደረሰባቸውን ለመግለጥ ያፍራሉ፥ ይፈራሉ። በባህላዊው ይሉኝታና ሌሎች ሌሎች ምክንያቶች ተሸብበዋል። በዚህ መካከል ድፍረቱ በድፍረት ሳይቆጠር፣ የማስተዋል ችሎታችንን በሚደፍር አገላለጥ አደባባይ ወጥቶ የሚሰድብን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዶ/ር ተዎድሮስ አድሃኖም ሆኗል።

ዶ/ር ቴዎድሮስ እንደሚነግረን አቶ አንዳርጋቸው ጽጌን እያንሸራሸረ በኢትዮጵያ የተሰራውን የልማት ስራ ሁሉ እያስጎበኘ ነው። በናዝሬት መንገድ ላይ ያለውን ግዙፍ የልማት ስራ አስጎብኝተውታል (የትግራይ አይሻልም ነበር?)። አንዳርጋቸው ደግሞ በዚህ ሁሉ ተመስጦ ኮምፒውተር እንዲሰጠው ጠይቆ መጽሃፍ ኣየጻፈ ነው። (ስላሴ ቅኔ አይሻልም ነበር?)

ቴዲ በአሜሪካ ድምፅ ራዲዮ ላይ እንዲህ ያለ አዛባ ጥሎ ደህና እንድንነጋገርበት አስችሎናል።

በብላቴን ጌታ ህሩይ፣ በሎሬንዞ ታእታዝ፣ በ አክሊሉ ሃብተወልድ፣ በዘውዴ ገብረ-ህይወትና ዘውዴ ገብረስላሴ፣ በይልማ ደሬሳ፣ በሃዲስ አለማየሁ ወንበር ላይ የተቀመጠው ቴዎድሮስ! የእኛንም ዘመን ጎሹ ወልዴን በኩራት እንጠቅሳለን!

ወያኔዎች መንግስት በያዙ ሰሞን፣ “ማዕከላዊ” ይባል በነበረው የምርመራ ማዕከል የታወቀ ገራፊ በቴሌቪዥን አቅርበው ለፕሮፓጋንዳቸው ተጠቅመዋል። “ውቃው” እየተባለ ይጠቀስ የነበረው “ገራፊ” ሲል የነበረውን ታስታወሳላችሁ? “ለምርመራ የሚቀርቡ ሰዎችን እንዲያውም ሻይና ቡና ኣየጋበዝሁ… በወንድማዊ ስሜት …” ይል ነበር። ቴዲ የረሳው “አንዳርጋቸውን ማታ ማታ ሸራተን ሆቴል ኣየጋበዝን … ራትና ሻምፓኝ እየ…” ስንቱን … ሲናገር ኣንዲህ ያለውን … ነገር ለምን ረሳ? በነገራችን ላይ እኔና ልጄ የምናውቀው አንድ ደራሲ በመጽሃፉ ውቃውን በማሰብ፣ “ደርግ በውሃ አጥምቆአል። ኣውነተኛው በእሳት የሚያጠምቀው በጊዜ ማህፀን ውስጥ ነበር። እነሆ ወያኔ ኢህአዴግ!” የሚል ቋንቋ ተጠቅሟል። (ከትዝታ በትዝታ የጠቀስኩት ነው።)

በዚህ ዘመን ከተገኙ ጀግኖች እናንተን በማስፈቀድ “አውራ ጀግናችን” የምለው አንዳርጋቸው እዉን መጽሃፍ ጻፈ? ይጽፋል? ወይስ አያ በረከት በሩን ዘግቶ ሁለተኛውን “ የሁለት ምርጫዎች ወግ” እየጻፈ ነው? የመጀመሪያ አልባረቀም ወይ? አለዚያ ሁላችንም እንደበረከት አድናቂና ብር ሰፋሪ አረብ ሳናነብና ሳይነበብልን እንድናደንቀው ልንገደድ ነው? (የበረከትን “ታላቅና ድንቅ” መጽሃፍ ባያነብበውም ኣንዳነበበው እንዲቆጠርለት የፈለገው ማን ነበር? የታላቁን ነቢይ ስም በመጠቀሙ ሆዴን ያመኛል።)

አንዳርጋቸው ጽጌ ያለበትን ሁኔታ የምናውቅ ይመስለኛል።

– ከአመት በላይ አካላዊና ሳይኮሎጂካል ግርፋትና እንደጥፍር መነቀል፣ መድፈቅና ሌላ ሌላው ስቃይ እንደደረሰበት ገጹና አነጋገሩ በግልጽ ይመሰክራሉ።

– የጄኔቫ ኮንቬንሽንና ሌሎች አለም አቀፍና ወያኔዎች ያወጡአቸው ህግጋትና ድንጋጌዎች ከሚያዝዙትና ከሚያራምዱት ውጭ ግለሰቡን ከጠበቃ፣ ከህጋዊ አማካሪዎች፣ ከቤተሰብ … አርቀው አስረዋል። አያያዙም ኢንተርናሽናል ውንብድና ነው።

– የፖለቲካ አክቲቢስቶች ከሆኑ ዳኞች ዘንድ እንኳን ያልቀረበ በመሰረቱ የጦር ምርኮና ነው፥ እነሱ እንዳቀረቡት።

– የእንግሊዝ አምባሳደር እንደምንም ብለውና ምን አልባትም የእንግሊዝ መንግስት አጠንክሮ በማስፈራራት አንዳርጋቸውን አነጋግረውታል። ለሰውየው በሰጠው ምላሽ ሞት ለእሱ በጣም እንደራቀና የሚፈልገውና የሚመኘው “ ሞትን” መሆኑን ገልጦላቸዋል። ይህንን ነው መጻሕፍት የሚወጡት የስቃይ ድምፅ ያልሁት። ወያኔዎች ከገባቸው ዛሬውኑ በወያኔዎችና በህዝባችን መካከል ወደመጨረሻው መተላለቅ የሚያመራ በሆነ ነበር። እግዚአብሄር ይመስገን ህዝባችን አልተጣደፈም።

– ከአምባሳደሩ ጉብኝት በኋላ የወጣው መግለጫ ይህ የእነ ቴዲ መንግስት በአስቸኳይ አንዳርጋቸውን አንዲፈታና ለደረሰበት የህሊናና የአካል ስቃይ ካሳ እንዲከፈል ነው።

እኔ ብሆን እነዚህንና የመሳሰሉትን ጥያቄዎች በአደባባይ የምናውቃቸውን ጉዳዮች አነሳበት ነበር። ቴዎድሮስ አድሃኖምን በመሰረቱ ኣንዲያደግ የሚሻ የዋህ ማይም ይመስላል። ይሁንና አደባባይ ይዞ የሚወጣው ነገር ሁሉ እድገቱን የሚቀጭ ነው። ከቶዉንም ይኽ የሚጠቀስበትን ለሃኪሞች የሚገባ ስያሜ ከየት እንዳመጣ እጠይቃለሁ። አበበ ገላውን።

አንዲት ተናጋሪ ወፍ እንዲህ ያለ ወግ አላት። የእንግሊዙ ኦክስፎርድ ዩኒቨርስቲ የፍልስፍና ፕሮፌሰር ለተማሪያቸው አንድ ጥያቄ አቅርበውለት መልሱን ይጠብቃሉ። ፕሮፌሰሩ ለፒኤችዲ ዲግሪው የመጨረሻ ፈተና ከተቀመጠው ወጣት ብዙ የምርምር ውጤቶችንና ረቂቅ የፍልስፍና ትንተና ይጠብቃሉ። እርግጥ መልስ ተሰጥቶአልና በየገጹ ቀያይ መስመሮች አጋድመዋል። እዚህም እዚያም። ተማሪው ይሞግታቸዋል። “ውሸት ነው፣ ትክክል መልስ አልሰጠህም ነው የሚሉኝ ሲል” ወዳጄ የጻፍኸውንም ሁሉ አንብቤአለሁ። ይሁን ኣንጂ “ውሸት ነው የጻፍከው። ዋሾ ነህ” የሚል ክብር ልሰጥህ አልችልም። አሉ የሚል አሳብ ከአንድ የኦክስፎርድ ዩኒቨርስቲ መጽሄት አንብቤአለሁ። ታዲያ ይፈቀድልኝና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትራችንን “ውሸት ተናግረዋል። ቀጣፊ ነዎ! አወናባጅና ዋጋ የማያወጣ ነገር ይዘው ገበያም ሆነወደ አደባባይ አይወጡ” ማለት ይቻላል። ደስ የሚለው የኦክስፎርዱ ፕሮፌሰር መግለጫ ነው “ዋሾ የሚል ክብር አልሰጥህም” ከዚያ በታች ምን አለ? ቢንጎ!

አለምነህ ዋሴ “ለመጀመሪያ ጊዜ”በይፋ ከሴት ጋር ስለተዳረችው ኢትዮጵያዊቷ ቤተልሄም ይርጋ ዘገበ

$
0
0

በሰሜን አሜሪካ በሁሉም ስቴቶች ተመሳሳይ ጾታ ጋብቻ ከተፈቀደ በኋላ አለምነህ ዋሴ ኢትዮጵያዊቷ ለመጀመሪያ ጊዜ በይፋ ከሴት አጋሯ ጋር ጋብቻ ፈጸመች ሲል ዘግቧል:: በድምጽ ያዳምጡት::

አለምነህ ዋሴ ለመጀመሪያ ጊዜ በይፋ ከሴት ጋር ስለተዳረችው ኢትዮጵያዊት ዘገበ

የአሳ ክትፎ አሰራር (Video)

$
0
0

መልክ በጉሮሮ ይገባል ይባላል:: ጤናማ ምግብ መመገብ ጤናማ ያደርጋል:: አሳ ለጤና ያለውን ጠቀሜታ ከዚህ ቀደም ብዙ ጊዜ አስተምረናል:: ዛሬ ደግሞ የአሳ ክትፎ አሰራርን አቅርበንላችኋል:: የ እህትቻንን ትምህርት በቭድዮ ተከታተሉት::

የአሳ ክትፎ አሰራር (Video)

የዘ-ሐበሻን የ2015 ዓመቱ ምርጥ ሰው ይምረጡ

$
0
0

zehabesha Person of The Year
ዘ-ሐበሻ በየዓመቱ እንደምታደርገው የአንባቢዎቿን ድምጽ በመሰብሰብ ለኢትዮጵያውያን ዘመን መለወጫ በዓል ዋዜማ የዓመቱን ምርጥ ኢትዮጵያዊ ትሸልማለች:: ወደ ኋላ መለስ ብለን እስካሁን በዘ-ሐበሻ አንባቢዎች የዓመቱ ምርጥ ሰውን ክብር በተከታታይ ዓመታት ያገኙት መምህር የኔሰው ገብሬ;  ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ;  አንዱአለም አራጌ  እና  አብርሃ ደስታ  ነበሩ::

የዘንድሮውስ የዘ-ሐበሻ የዓመቱ ምርጥ ሰው ማን ይሁን? – ምርጫዎትን ከጥቂት ምክንያቶች ጋር አብረው በinfo@zehabesha.com ኢሜይል ወይም facebook.com/zehabesha ያሳውቁን:: በመደበኛ ስልክ ወይም በቫይበር በስልክ ቁጥር 612-226-8326 ወይም በስልክ ቁጥር 612-986-0557 ቴክስት ማድረግ ይቻላል::

ከሰሜን አሜሪካ ውጭ ያላችሁ ሰዎች በስልክ ቴክስት ለማድረግ ከፈለጉ ከፊት ለፊት የአሜሪካንን ማዞሪይ 01 ማስገባትዎን እንዳይረሱ:: የዘ-ሐበሻን የዓመቱ ምርጥ ሰው ይምረጡ::

ዘ-ሐበሻ ዕውነት ያሸንፋል!!

Sport: የፕሪምየር ሊጉ መክፈቻ –ቸልሲ ታሪክ አመለጠው

$
0
0

MAN UNITED 1-0 TOTTENHAM
ከጨዋታ በኋላ በኳስ ሜዳ
በእንግሊዝ ፕሪምየር ሊግ መክፈቻ፡-

የጨዋታ ውጤት፡
ማንችስተር ዩናይትድ 1-0 ቶትንሃም
ቦርንማውዝ 0-1 አስቶን ቪላ
ኤቨርተን 2-2 ዋትፎርድ
ሌስተር 4-2 ሰንደርላንድ
ኖርዊች 1-3 ክሪስታል ፓላስ
ቼልሲ 2-2 ስዋንሲ

ቼልሲ ዛሬ በስታምፎርድ ብሪጅ ስዋንሲን ቢያሸንፍ ኖሮ 16 የመክፈቻ ጨዋታዎችን በማሸነፍ አዲስ ክብረ ወሰን ያስመዘግብ ነበር። አሁን 15 የመጀመሪያ ጨዋታዎችን በማሸነፍ ከማንችስተር ዩናይትድ ጋር ክብሩን ይጋራል።

ቡድናቸው ማንችስተር ዩናይትድ ቶትንሃምን 1-0 የረታላቸው ሉዊ ቫንሃል ድሉ የልደት ስጦታ ሆኖላቸዋል። ከ1993 ወዲህ በልደታቸው ቀን ድል ሲቀናቸው ዛሬ የመጀመሪያው ነው። ጨዋታው ሲጠናቀቅ ከቢቲ ስፖርት ጋር በነበራቸው ቆይታ 64ኛ ዓመት ልደታቸውንም ድሉንም በሚወዱት ሬስቶራንት እንደሚያከብሩት ተናግረዋል።

የቼልሲው ግብ ጠባቂ ኩርቶዋ በአዲሱ የፕሪምየር ሊግ የመጀመሪያ ቀይ ካርድ ያየ ተጫዋች ሆኖዋል። በቀዩ ካርድ ምክንያት በቀጣዩ ሳምንት ከማንችስተር ሲቲ ጋር አይሰለፍም።

ኦፊሴላዊ በሆነ ውድድር ላይ ለማንችስተር ዩናይትድ በመጫወት ባስትያን ሸዋንስታይገር የመጀመሪያው ጀርመናዊ ሆኖዋል።

ካይሊ ዎከር በራሱ ጎል ላይ ያስቆጠረው እና በአዲሱ የውድድር ዓመት የፕሪምየር ሊጉ የመጀመሪያ ጎል ሆኖ ለማንችስተር ዩናይትድ የተመዘገበው ጎል በፕሪምየር ሊግ ታሪክ በመክፈቻ ጨዋታ በራስ ላይ የተቆጠረ የመጀመሪያ ጎል ሆኖዋል።

አምስት ተጫዋቾች ከቶትንሃም ጋር በነበረው ጨዋታ ላይ ለመጀመሪያ ጊዜ በውድድር ጨዋታዎች ለማንችስተር ዩናይትድ የመሰለፍ ዕድል አግኝተዋል። ፈረንሳዊው አማካይ ሞርጋን ሸንደርሊን፣ ሆላንዳዊው አጥቂ ሜምፊስ ዲፔ፣ አርጀንቲናዊው ግብ ጠባቂ ሰርጂዮ ሮሜሮ፣ ጣልያናዊው የመስመር ተከላካይ ማቲዮ ዳርሚያን እንዲሁም ተቀይሮ የገባው ሽዋንስታይገር። በጨዋታው ማንችስተር ዩናይትድ ያን ያክል ባይሆንም አሰልጣኝ ልዊ ቫንሃልን ጨምሮ ብዙዎች የ25 ዓመቱ የመስመር ተከላካይ ማቲዮ ዳርሚያን ባሳየው እንቅስቃሴ ተደስተዋል።

ከዋሽንግተን ዲሲ የጋራ ግብረሃይል የተሰጠ መግለጫ –“ያለነጻነት ፍትሕ የለም”

$
0
0

ሐምሌ ፴ ፳፻፯

በኢትዮጵያ አገራችን ፍትሕ ትንሽ ትልቁ ሙስሊም ክርስቲያን ሳይል ጥማቱን ከንግግር አልፎ በየአብያተ ክርስቲያናት ጸሎታቸውን ፣ በየመስጊዶች ሶላታቸውንና ጸሎታቸውን የሚያሳርጉት ስለ ፍትሕ በመጮህ ነው።የጥንቱን ታሪክ እንዳለ ብናቆየው እንኳ ባሳለፍነው ከሬት የመረረ ወያኔያዊ ስርዓት ፍትሕ በእውን ተከስታ ልትታይ ቀርቶ በዳሰሳና በሽታ እንኳ ደብዛዋ ጥፍቶ የ፺ ሚሊዮን ህዝብ የምኞት መዝሙር ሆና ፳፭ አመታትን አስቆጠረች። ዛሬም የፍትሕ ያለህ የሚለው የህዝባችን ጥያቄ ከዳር እስከ ዳር ቀጥሏል።

Ginbot 7

በርካቶች ህግ በማይከበርበት ፍርድ ቤት በወያኔ ተከሰው በወያኔ ተመስክሮባቸው በወያኔ ዳኛች፣ በወያኔ አቃቤ ህጎች፣ በወያኔ የግፍ ሰንሰለት አሳራቸውን የበሉ በዚያውም ያሸለቡ ደብዛቸው የጠፋ ቤቱ ይቁጠራቸው ለማለት ተገደናል። ለአሁኑ ግን በኢትዮጵያ ሙስሊሞች ላይ ሰሞኑን የተጠበቀ ምክንያቱም ወያኔ ከሚዘውረው ፍርድ ቤት ፍትህ ስለማይጠበቅ ነገር ግን የኮሚቴውን ንጹህነት የሚያውቅና ኮሚቴውን ነጻ ከማሰናበት ሌላ ላልጠበቀ ህዝብ በጣም አስደንጋጭ ነው። ስለሆነው በንጹሃን የሙስሊሙ መፍትሄ አፈላላጊዎች ላይ የተበየነውን ፍርደ ገምድል ብይን ለመቃወም እናም ለተበየነባቸው ጀግኖቻችን ሳይሆን ላንተ ይብላን ወያኔ ለማለት እንወዳለን። ከ፺፯ ዓመተ ምህረት ምርጫ ህዝባዊ እንቅስቃሴ በኋላ በሃይል ተጨፍልቆ ብልጭ ብልጭ ሲል የከረመው ህዝባዊና ኢትዮጵያዊ ወኔ ድንገት ሰሜን ምዕራብ አዲስ አበባ ከዓወሊያ ተቋም ገንፍሎ ምድሪቷን ያጥለቀለቀው የኢትዮጵያ ሙስሊሞች ትግል ስንቃኘው እንደዜጋ አድናቆት ስንቸረው በመብት ትግሉ ህይወት ያስከፈላቸውን አሳሳ፣ገርባ፣ኮፈሌዎችን፣እንዲሁም በፈሪ በትር የተቀጠቀጡትን አካል የጎደለባቸውን፣ ባኑዋር መስኪድ የጥቁር ሽብር ሰለባ የሆኑትን፣ለፍትሐዊ ትግሉ በህዝብ ተወክለው ህዝቡ ለጠየቀው ፫ ጥያቄዎች ከ፯ እስከ ፳፪ አመት ከመድረክ ጀርባ በተዘጋጀው የቀልድ ቲያትር መጋረጃ የሀሰት ፍርድ ለተወሰነባቸው ወንድሞቻችን እና እህቶቻችን ታላቅ ወገናዊ አክብሮት እንሰጣቸዋለን።

ትግሉ የጋራ ነው ድሉም እንደዚሁ፤ እኛ በዋሽንግተን ዲሲ አካባቢ የምንገኝ የጋራ ግብረ ሃይል በዚህ ሳምንት የሰማነው በባህሪው እውነት ከማያውቀው የወያኔ ፍርድ ቤት የጠበቅነው ነውና ባንደነቅም ሆኖም ግን እንዲህ አይነት በ፺ ሚሊዮን ህዝብ ላይ የተቀለደ ቀልድን በቀላሉ አንመለከተውም፤እንዲሁም ለጀግኖቹ ንጹሀኖች ፈጣሪ ያበርታቸው፣ቤተሰቦቻቸውን አምላክ ያጽናናቸው ስንል ለኢትዮጵያ ሙስሊሞች ባጠቃላይ አብሽሩ የሚል መልዕክት እናስተላልፋለን።

ፍትሕ የተዘነበለችው ባጠቃላይ በኢትዮጵያውያኖች ላይ ነውና ለዚህ ሁሉ አብነቱ የፍትሕ ያለህ የሚል ጩኸታችን የሚቆመው ይህ ጸረ እስላም፣ጸረ ክርስቲያን፣ ጸረ አገር የሆነው ሰይጣናዊ ስርዓት በጸሎትም፣ በሁለገብ ትግልም፣ በተባበረ ህዝባዊ እምቢታም ተመንግሎ ነጻነታችንን ስንጎናጸፍ ብቻ ነው ብለን እናምናለን።ለዚህም በኛ በኩል ሰላም ላጣው ህዝባችን፣ፍትሕ ለጠፋበት ወገናችን፣በኩልነት ለምታኖረን ኢትዮጵያችን፣ ለሀይማኖት ክብራችን ባስገባን ቀዳዳ ሁሉ ገብተን የመጨረሻዋ እስትንፋሳችን እስክትቆም ድረስ አብረን ተባብረን ለመታገል በጋራ እንነሳ እንላለን።

ፈጣሪያችን አገራችንን ይጠብቅልን!!!

ኢትዮጵያ በክብር ለዘላለም ትኑር !!!
የዋሽንግተን ዲሲ የጋራ ግብረ ሃይል dcjointtaskforce@gmail.com


አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ፍርድ ቤት ያልቀረቡበትን ምክንያት የማረሚያ ቤት ኃላፊ ቀርበው እንዲያስረዱ ታዘዘ

$
0
0

በሽብርተኝነት ተጠርጥረው ክስ የተመሠረተባቸው እነ ዘመነ ካሴ በመከላከያ ምስክርነት የቆጠሯቸውና ለሦስት ጊዜያት የተጠሩት አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ፣ ሐምሌ 29 ቀን 2007 ዓ.ም.ባለመቅረባቸው የፌዴራል ማረሚያ ቤት ኃላፊ ያልቀረቡበትን ምክንያት ፍርድ ቤት ቀርበው እንዲያስረዱና ምስክሩንም እንዲያቀርቡ ሌላ ትዕዛዝ ተሰጠ፡፡

andargachew new picture

በሽብር ድርጊት ወንጀል ተጠርጥረው ዓቃቤ ሕግ ክስ የመሠረተባቸውን የእነ ዘመነ ካሴን ክስ እየመረመረ የሚገኘው የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 19ኛ ወንጀል ችሎት፣ ለሐምሌ 29 ቀን 2007 ዓ.ም. አቶ አንዳርጋቸውን መቅረብ አለመቅረባቸውን በችሎት ሲያረጋግጥ ግለሰቡ አልቀረቡም፡፡ ለምን እንዳልቀረቡ የማረሚያ ቤት ተወካይ ቀርቦ እንዲያስረዳ ፍርድ ቤቱ ቢጠይቅም ማንም ምላሽ ሊሰጠው አልቻለም፡፡

ፍርድ ቤቱ ሌላ ትዕዛዝ ሊሰጥ ሲል ከተከሳሾቹ አንዱ ተነስተው ማረሚያ ቤቱ የተለያዩ ምክንያቶች እየሰጠ መሆኑን ገልጸው፣ አቶ አንዳርጋቸውን የያዛቸው የፀረ ሽብር የጋራ ግብረ ኃይሉ በመሆኑ ማረሚያ ቤቱ የማያቀርብ ከሆነ ለእሱ ደብዳቤ እንዲጻፍላቸው ጥያቄ አቅርበዋል፡፡

ተከሳሹ በመቀጠልም፣ ‹‹ተከሳሹ ፍርደኛ ነው፡፡ ፍርደኛ ደግሞ የሚኖረው ማረሚያ ቤት ነው፡፡ ለምን ማረሚያ ቤቱ እንዲያቀርብ ጥብቅ ትዕዛዝ አይሰጠውም?›› በማለት ጠይቀዋል፡፡ ከታሰሩ ሦስት ዓመታት እንደሞላቸው በመግለጽ ቤተሰቦቻቸው ‹‹የአሸባሪ ቤተሰብ›› እየተባሉ የሚያከራያቸው በማጣታቸው፣ በየቦታው ተበትነው እየተሰቃዩ መሆኑን በመናገር ፍርድ ቤቱ አቶ አንዳርጋቸው በአጭር ቀጠሮ ቀርበው እንዲመሰክሩላቸው ጠይቀዋል፡፡

ፍርድ ቤቱ እስከ ነሐሴ 15 ቀን 2007 ዓ.ም. ድረስ ብዛት ያላቸው ምስክሮችን እንደሚሰማና በአጭር ቀናት ማቅረብ እንደማይችል ገልጾ፣ ለጥቅምት 12 ቀን 2008 ዓ.ም. ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡

አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ በመኪና ሆነው አገሪቱ በልማት እያደረገች ያለውን ግስጋሴ እየጎበኙ መሆኑን፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖም በቅርቡ መናገራቸውን የአሜሪካ ድምፅ ሬዲዮ መዘገቡ ይታወሳል፡፡

Source: Ethiopian Reporter Newspaper

ሰበር ዜና –ሪያድ ከተማ በሙስሊም ኢትዮጵያውያን ፀረ ወያኔ /ኢ.ህ.አ.ዴ.ግ ተቃውሞ ስትናጥ አደረች

$
0
0

sudi6(ዘ-ሐበሻ) ሰሞኑን የህወሃት/ኢ.ህ.አ.ዴ.ግ ፍ/ቤት በሙስሊሙ መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ አባላት ላይ የወሰደውን ኢፍተሃዊ ውስኔ በመቃወም ሪያድ ከተማ ውስጥ ትላንት አርብ ኦገስት 7 2015ምሸት ኢትዮጵያዊው ህዝበ ሙስሊም አንድነቱን ጠብቆ ተቃውሞውን አሰምቷል ። ቁጥሩ ከፍተኛ እንደሆነ ህዝብ የተገኘበት  ይህ ታላቅ ተቃውሞ የአካባቢውን ድባብ ለውጦት እንደነበር ለማወቅ ተችሏል። የተከሰተው ነገር በራሳችን እንደደረሰ ተሰምቶን በሶስት ቀን ውስጥ በተጠራ የተቃውሞ ጥሪ ይህን ያህል ህዝብ አንድነቱን ጥብቆ ለተቃውሞ በነቂስ መውጣቱየትግሉ አንዱነት ጥንካሬ መገለጫ መሆኑን የገለጹት ሼክ ሲዒድ አህመድ ህዝበ ሙስሊሙ በመንግስት ከባድ ፈተና እንደ ተጋረጠበት አውስተው ይህ ፈተና አዲስ ሆኖብን ሳንደናገጥትግሉን በበሰለና በስለጠነ መንገድ በማጠናከር እስከ ድል መቀጠል እንደሚገባ በቁጣ የወጣውን ህዝብ ሙስሊም በማረጋጋት በአባታዊ ምክራቸውን ገስጸዋል ።

ሼክ ሰዒድ በማስከተል አቡበከር በአንድ ወቅት በመንግስት ፀጥታ ሃይሎች ወህኒቤት ግፍ እይተፈፀመበት  « ፍ/ቤቱም የኛ ፤ ፖሊሱም የኛ ፤ አቅቤ ህጉም የኛ ፤ መርማሪውም የኛ ስለሆነየፈለከውን የመከላከያ ምስከር ብታመጣ ብትወጣ ብትወርድ ከፍርድ አታመልጥም እኛ ነን የምንፈርድብህ » ተብሎ በስረአቱ ካድሬዎች በምጸት ከፍርድ ቤቱ ውሳኔ በፊት ተነግሮትየነበረውን በተግባር ማየቱን ሼኩ ለተስብሳቢው በመጥቀስ በመሪዎቻችን ላይ የተፈፀመው ደባ ሊያስደንቀን እንደማይገባ ገልጸው የፍ/ቤቱን ኢፍታሀዊነት ለተሰብሳቢው በተጨባጭ አስረድተዋል። በውቅቱ በቁጣ ገንፍሎ የወጣውን ህዝብ ለማስተናገድ ተይዞ የነበረው ቦታ በመጨናንቁ የነበረውን የሪያድ የአየር ሙቀት በመቋቋም ከ ምሽቱ 1 ስዓት ጀምሮ እስከ ሊሊቱ9 ስዓት ድረስ በዘለቀው በዚህ  ፀረ ጭቆና ህዝባዊ ተቃውሞ ላይ አንዳንድ የስብሰባው ተሳታፊዎች  ህዝበ ሙስሊሙን በገዛ ሃገሩ መቆሚያ መቀመጫ ያሳጣውን የህወሃት/ኢ.ህ.አ.ዴ.ግስረዓት እንዲያጠፋላቸው እያለቀሱ  ለፈጣሪያቸው  ፀሎት  «  ዱአ » አድርሰዋል ።  ሰሞኑን የህወሃት/ኢ.ህ.አ.ዴ.ግ መንግስት ፍ/ቤት በህዝበ ሙስሊም ተወካዮች ላይ ያሳለፈው ውሳኔሰረዓቱ በመላ ኢትዮጵያዊ ሙስሊም ላይ እየፈጸመ ያለው ሃይማኖታዊ ጭቆና ግፍና በድል አንዱ አካል መሆኑን የገለጹት እንዚህ የስብሰባው ተሳታፊዎች ከእንግዲህ ትዕግስታቸውመሞጠጡን ጠቅሰው  በዚህ አምባ ገነን ስረዓት ላይ የጀመሩትን ትግል እስከ መጨረሻ አጠናክረው ለመቀጠል በመወሰን የአቋም መግለጫ አውጥተዋል።

በሳውዲ አረቢያ ድምጻችን ይሰማ ደጋፊዎች እያካሄዱ ባለው ሃይማኖታዊ ፀረ ጭቆና ትግል የህወሃትን/ኢ.ህ.አ.ዴ.ግን ስረዓት የቦንድ ሽያጭና መስል የስረአቱን እንቅስቃሴበማሽመድመድ  የታወቁ  ግንባር ቀደምና ጠንካራ መሆናቸው  ይነገራል።  ኢንጂነር መሃመድ አባስ ከሪያድ ሳውዲ አረቢያ

የህወሓት‬ አገዛዝ በላይ አርማጭሆ የጀመረው የትጥቅ ማስፈታት ዘመቻ አሁንም ተጠናክሮ እንደቀጠለ ነው

$
0
0

clash

የአርበኞች ግንቦት 7 ድምጽ እንደዘገበው አርበኞች ግንቦት 7 ጦርነት በከፈተባቸውና አሁንም እየተፋለመባቸው በሚገኙ አካባቢወች የሚኖሩ ደሀ ገበሬዎች ለንብረታቸው መጠበቂያ ጥረው ግረው ጥሪታቸውን በማሟጠጥ በገንዘባቸው ገዝተው በፈቃድ የታጠቁት የጦር መሳሪያ በህወሓት አገዛዝ እየተወሰደባቸው ይገኛል፡፡
ሰሞኑን በታች አርማጭሆ የተጀመረው ትጥቅ የማስፈታት የህወሓት መሰሪይ ተግባር ላይ አርማጭሆንም ጨምሮ ተጠናክሮ ቀጥሏል፡፡
በአጠቃላይ በአርማጭሆ እና በወልቃት ምድር ሰፍሮ የሚገኘው ህወሓት መራሹ መከላከያ ሰራዊት በህጋዊ መንገድ የታጠቀውን ገበሬ የጦር መሳሪያ መግፈፍ ዋነኛ ስራው ሁኗል፡፡

ላይ አርማጭሆ ከች ከንፈታ ቀበሌ ፈረስ ማጎሪያ ላይ ሰፍሮ የሚገኘው በህወሓት ቁጥጥር ስር የሚገኘው መከላከያ ሰራዊት ሰበብ አስባብ እየፈለገ የአካባቢውን ገበሬዎች ትጥቅ በመንጠቅ ስራ ላይ ተሰማርቶ ይገኛል፡፡
የህዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ ዘረኛ ቡድን ይቃወሙኛል ብሎ ከሚሰጋቸው ደሀ ገበሬዎች የሚነጥቀውን የጦር መሳሪያ ደጋፊዎቼ ናቸው ለሚላቸው ግለሰቦች እያስታጠቀ እንደሚገኝ የአርበኞች ግንቦት 7 ድምፅ ሬድዮ ዜና ምንጮች ገልፀዋል፡፡
አርበኞች ግንቦ 7 በጎንደርና አካባቢው በህወሓት መራሹ መከላከያ ሰራዊት ላይ እየፈፀመው የሚገኘውን ጥቃት እና እያገኘ የሚገኘውን ሰፊ የህዝብ ድጋፍ ተከትሎ በሰ/ጎንደር ዞን አስተዳደር የህወሓት አገልጋይ በሆኑት ከፍተኛ ሹማምንቶችና የበታች ካድሬዎች መካከል ከፍተኛ ፍጥጫ ተፈጥሯል፡፡
የላይኞቹ የህወሓት አገልጋዮች ከከፍተኛ የህወሓት ባለስልጣናት የተሰነዘረባቸውን “የጎንደር ህዝብ እኛን ጠልቶ ለምን ከአርበኞች ግንቦት 7 ጎን ተሰለፈ?” የሚል ጥያቄ ለበታቾቻቸው በተለያዩ የግምገማ መድረኮች በማንሳታቸው ምክንያት ነው ፍጥጫው የተከሰተው፡፡

በባህር ዳር ቀበሌ 11 ወጣቶችና በፖሊሶች መካከል ግጭት ተፈጠረ * አባላቱ በገፍ እየከዱት በሚገኘው አየር ኀይል አለመተማመኑ ስር ሰዷል

$
0
0
Photo File

Photo File

አርበኞች ግንቦት 7 ድምጽ እንደዘገበው የባህር ዳር ከተማ ቀበሌ 11 አባይ ማዶ ወጣቶች አንድ አካባቢ ላይ ተሰባስበው በመጫወት ላይ እያሉ ፖሊሶች ድንገት መጥተው “ለምን አንድ ላይ ተሰብስባችሁ ቆማችሁ?” በማለት አምባጓሮ በመፍጠራቸው ነበር ግጭቱ የተነሳው፡፡
ፖሊሶቹ ወጣቶችን ከቆሙበት በኃይል አባረው ወደየቤታቸው ለማስገባት ሲሞክሩ ወጣቶቹ በፖሊስ ላይ የአጸፋ እርምጃ በመውሰዳቸው አንድ ፖሊስ ለከፋ ጉዳት እንደተዳረገ ታውቋል፡፡
የህወሓት አገዛዝ ለስልጣኑ የሚያሰጋውን የህብረተሰብ ክፍል እየመረጠ ትጥቅ ማስፈታቱን አጠናክሮ ቀጥሏል፡፡
የህዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ አምባገነናዊ ስርአት የግብአተ መሬት ጊዜውን በጥቂቱም ቢሆን ያራዝምልኛል ብሎ ከነደፋቸው እቅዶች መካከል አንዱ የሆነውን ህዝቡን ትጥቅ የማስፈታት ተግባር በታች አርማጭሆ ገበሬዎች ላይ በተለየ ሁኔታ በግፍ የሚያስታጥቀው የህብረተሰብ ክፍል ያለው ዘረኛው የህወሓት ቡድን በአማርኛ ተናጋሪው ገበሬ ላይ አሁን እየፈፀመ የሚገኘው የትጥቅ ገፈፋ ከዚህ ቀደምም በተደጋጋሚ ሲያደርገው የቆየው መሆኑ ይታወቃል፡፡
አባላቱ በገፍ እየከዱት በሚገኘው አየር ኀይል ውስጥ ተፈጥሮ የቆየው አለመተማመን ስር ሰዶ ከፍተኛ ደረጃ ላይ መድረሱ ታወቀ፡፡
ለሰላም ማስከበር ተልኮ ወደ ደቡብ ሱዳን ሊሄዱ የተመለመሉት የአየር ሀይል አባላት የደቡብ ሱዳን ጉዞ ተሰርዞ ወደ ሱማሊያ እንደሚሄዱ ስለተነገራቸውና በግምገማ በመወጠራቸው ምክንያት በርካታ አብራሪዎች፣ ቴክኒሻኖች እና ሌሎች የተለያዩ ክፍሎች ድጋፍ ሰጭ ሰራተኞች በመክዳት ላይ ናቸው፡፡
በመሆኑም በአየር ሀይል ውስጥ አለመተማመኑ ገደቡን አልፎ አብራሪዎች ለልምምድ በሚያበሩት አውሮፕላን ውስጥ የህወሓት አባላት ከጎን እንዲቀመጡ እየተደረገነው፡፡ በተጨማሪም አብራሪዎች ነዳጅ በሚሞሉበት ጊዜ ከፍተኛ ቁጥጥር እየተደረገባቸው ይገኛል፡፡

እየተቃወሙ ለመኖር…….!     ይገረም አለሙ

$
0
0

 

Arbegoch Ginbot 7የአርበኞች ግንቦት 7 ቃልን ወደ ተግባር የማሸጋገር እንቅስቅሴ ያሸበረው ወያኔን ብቻ አለመሆኑን ከተቃውሞው ጎራ ከሚሰማው የተቀዋሚ ተቀዋሚዎች ጩኸት እያየን ነው፡፡ ርጥቡ ሬሳ ደረቅ ያስነሳ አንዲሉ ይህ ሰሞነኛ ጩኸት የተረሳ እንዲታወስ የተተወ እንዲቀሰቀስ ምክንያት ሆኖ የአንዳንዶቹ ጯሂዎች የትናንት ማንነት ድብቅ ዓላማና ፍላጎት ጭምር  ጸሀይ እንዲሞቀው እየተደረገ ነው፡፡የማለባባስ አጉል ባህላችንን ተራምደው የይሉኝታ ገመዳችንን በጥሰው ስም እየጠቀሱ መረጃና ማስረጃ እያጠቀሱ አካፋን አካፋ ለማለት ለደፈሩ ወገኖቼ ያለኝን አክብሮት እገልጻለሁ፡፡ እያለባበስን አርባ አመት አልቅሰናልና በቃ ማለት ይኖርብናል፡፡

አደባባይ ወጥተው የሚጮኹትም ሆኑ ከኋላ ሆነው የሚገፉት የየግል ፍላጎታቸውም ሆነ  አንድ የሚያደርጋቸው ምክንያት ምንነትና አንዴትነት  በተለያዩ ሰዎች ተጽፋል፡፡ እውነት ናቸውና መስማማቴን እየገለጽሁ ያልተገለጸ የመሰለኝን ልጨምር፡

ስማቸው ብዙ ነው (ፖለቲከኛ ፣ጋዜጠኛ፣ነጻ ማህበር፣ወዘተ) መገኛቸው ሀገር ውስጥም ውጪም ነው፤ዓላማቸው ቢችሉ ምን-ይልክ ቤተ መንግሥት መታየት ካልሆነም በተቀዋሚነት ካባ አንድም ክብር ሁለትም ብር እያገኙ መኖር  ነው፡፡ ተባብሮ መስራት አይሆንላቸውም፡ እነርሱ የሚመሩት ወይንም በቀጥታም ሆነ በተዘዋወዋሪ የሚቆጣጠሩት ካልሆነ በስተቀር ማናቸውም ትግል (ሰላማዊውም የጠብ-መንጃውም) አንድ ርምጃ ሲራመድ ማየት አይፈልጉም፡፡

ሲያልሙት የኖሩትን ሥልጣን ለማግኘት የሚቻለው ደግሞ አንድም በምርጫ አንድም በጡንቻ ነው፡፡እነርሱ በሁለቱም መንገድ ለመሄድ አይችሉም፡፡(አንዳንዶቹ ሁሉን ሞክረው የከሸፈባቸው ናቸው፡፡) የምርጫው ነገር እንኳን ለእነርሱ ፓርቲ መስርተው በምርጫ ቦርድ ተመዝግበው መቀመጫቸውን ሀገር ቤት አድርገው ለሚፍጨረጨሩትም አልተሳካም፡፡ ሀገር ቤት በሚገኙ ተቀዋሚዎች ተከልለው ያደረጉት ሙከራም አልተሳካም፡፡ ( የኢትዮጵያ ዴሞክራሲዊ ኃይሎች ህብረት ይጠቀሳል) የጡንቻውን መንገድ ቢያልሙትም አልሆነላቸውም፤አይሆንላቸውም፡፡ ከሌሎች ጋር ተባብረው በተቀዋሚነት ተከብረው ለመኖር፤ ከተቻለም  ተከልለውም ቢሆን ወደ ምኒልክ ቤተ መንግሥት ለመድረስ መከጀላቸው ባይቀርም መሪነቱን እነርሱ ካልያዙት ወይንም እንቅስቃሴው በቀዳሚነት የእነርሱን ዓላማና ፍላጎት የሚያሳካ ካልሆነ በጅ አይሉምና፡ በዚህም መንገድ ስንዝር መራመድ አልቻሉም፤አይችሉምም፡፡

ስለሆነም ያላቸው ምርጫ ላለፉት ሀያ አመታት ሲተገብሩትም ያየነው ተቀዋሚ እየተባሉ መኖር ነውና በሰላማዊ ትግል በተአምር፣ ወይንም በተቃራኒው መንገድ በጦር  የወያኔ ሥልጣን ቢቀየር ይህን ስለማያገኙ ጠንከር ያለ እንቅስቃሴ ሲጀመር ፈጥነው ይዘምቱበታል፡መገንባቱን ሳይሆን ማፍረሱን፣ ማቀራረቡን ሳይሆን ማለያየቱን፤ መደገፉን ሳይሆን ማደናቀፉን የተካኑበት ናቸውና እስካሁን በአብዛኛው ተሳክቶላቸዋል፡፡ ዛሬ ግን ተነቅቶባቸዋልና ድብቅ ማንነታቸውን ያጋልጡ፣ ቀሪ ህይወታቸውን ያበላሹ  ለልጆቻቸው መጥፎ ስም ያቆዩ እንደሁ አንጂ የሚሳካላቸው አይመስለኝም፡፡

ፊሺካው ተነፍቷል ጦርነቱ ተጀምሯል በተባለበት ማግስት በፍጥነት ተጠራርተው ከጀመሩት ጫጫታ ውስጥ አንዳችም መፍትሄ ጠቋሚ ሀሳብ አለመኖሩ ከመነሻው በተቃውሞው ሰፈር ይገኙ እንጂ ለውጥ ናፋቂ ሳይሆኑ ወሬ አሟሟቂ፤ የተግባር ሳይሆን የምላስና የብዕር ታጋዮች  መሆናቸውን የመሰከረ ነው፡፡ ትናትም ሆነ ዛሬ ሰላማዊውንም ሆነ የጠብ-መንጃውን ትግል የሚቃወሙት ተቀዋሚ እየተባሉ ሆነው ሳይሆን እያስመሰሉ፣  እየታገሉ ሳይሆን እያውደለደሉ ክብርም ብርም የሚያገኙበት ሜዳ እንዳያጡ በመስጋት ነው፡፡  ግን ለምን? እነርሱ በተቃዋሚነት እንዲኖሩ የወያኔ እድሜ  መርዘም አለበት?  የኢትዮጵያ ሕዝብ በአንባ ገነን አገዛዝ ውስጥ መኖር አለበት ?ከእነርሱ ፍላጎትና ከሀገር ነጻነት የቱ ይበልጣል?፤የቱ ይቀድማል፡? በእውነቱ አሳፋሪም በታሪክና በትውልድ የሚያስጠይቅም እኩይ ተግባር ነው፡፡

ይህ አድራጎት ዛሬ የተጀመረ አይደለም፤ እንደውም ከአንዳንዶቹ ጋር አብሮ ያረጀ ነው፤ ትንሽ የቅርብ ግዜ ማሳያዎችን አንመልከት፡

ማሳያ አንድ፤  በ1992 ዓም ኢዴፓ የሚባል ፓርቲ ተመስርቶ በአጭር ግዜ ሰፊ እንቅስቃሴ አደረገና እውቅና አገኘ፤  በዚህ መልኩ እየገነነ ከቀጠለ በግልም ሆነ  በድርጅት እስከመኖራቸውም እንዳይረሱ የሰጉት እነዚህ የወያኔም የተቀዋሚውም  ተቀዋሚዎች የለመዱትንና የተካኑበትን የማደናቀፍ ዘመቻቸውን ከፈቱበት፤ የፓርቲው አመራሮች ቢቸግራቸው በእነዚህ ሰዎች በተወጠነውና በምድረ አሜሪካ በተዘጋጀ ጉባኤ ተካፋይ ሆነው የኢዴኃህ አባል ሆኑ፡፡ ሊቀመንበሩ ዶ/ር አድማሱ ገበየሁ የህብረቱ ዋና ጸኃፊ ለመሆን ቢበቁም  ከመነሻው የተገባው በእምነት ሳይሆን  የሰዎቹን አፍራሽ ዘመቻ በመፍራት ነበርና ብዙም ሳይቆይ ፓርቲው ከህብረቱ ወጣ፣ መኢአድ ለጉባኤ የላካቸው አባላቱ ሀገር ቤት ሳይመለሱ ነበር ጉባኤው በእነዚህ ሰዎች ሴራ መጠለፉን ገልጾ  የጉባኤውን ሂደት በመቃወም ጥያቄ አቅርቦ፤ጥያቄው ካልተመለሰ እንደማይቀጥል ያስታወቀው፡፡ ኢዴኃህም የቡና ውሀ ሆነ፡፡ (በምርጫ 97 የሰሩትም የሚረሳ አይደለም፡፡)

ማሳያ ሁለት ..ቅንጅት ሲመሰረት  መሪነቱን እንያዝ እንዳይሉ ከመስፈርቱ አንዱ በሀገር ቤት ያሉ የሚል በመሆኑ፣ እነርሱ ደግሞ አብዛኛዎቹ ከሀገር ውጪ ስለሚኖሩና  ሀገር ቤት ፓርቲ ስለሌላቸው አልተቻላቸውም፤ በእጅ አዙር አንዳይቆጣ ጠሩት ከቅንጅት የወቅቱ ጥንካሬ አንጻር ለዛ የሚያበቃ አቅም አልነበራቸውም፡፡ እናም በሚያውቁት በለመዱትና በተካኑበት ስልትና መንገድ ብዙ ዘመቱበት፤ ወዳጅ መስለው በመቅረብ መጥፎ እየመከሩ አቅጣጫ ለማሳት፣ በአመራሩ መካከል መጠራጠር ለመፍጠር ብሎም ቅንጅትን ከመረጠው ሕዝብ ለማጣላት ከውጪም በሀገር ውስጥም በመልእክተኞቻቸው በኩል ብዙ ሰርተዋል፡፡ የቅንጅት አመራሮች ለፓርላማ ሳይሆን ለወህኒ ሲዳረጉም ተደስተዋል፡፡

ማሳያ ሶስት፤የቅንጅት አመራሮች ከእስር ከወጡ በኋላ የፈጠሩት አለመግባባት እስከ መለያየት እንዲያደርሳቸው ከሁለቱም ወገን ደጋፊ መስለው በመሰለፍ የእብድ ገላጋይ ድንጋይ ያቀብላል አይነት የተጫወቱት አፍራሽ ሚና ቀላል አይደለም፡፡ ይህን ለማረጋገጥ በወቅቱ በዌብ ሳይቶች  በጋዜጦችና በማህበራዊ ድረ-ገጾች ወዘተ ላይ የተጻፉትን ማየት በየፓልቶኩ በያራዲዮው የተነገሩትን ማደመጥ በቂ  ነው፡፡

ማሳያ አራት፤  የቅንጅት ከፊሉ ወገን ተሰባስቦ ወ/ት ብርቱካን ሚደቅሳን ሊቀመንበሩ አድርጎ አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ የተሰኘ ፓርቲ መስርቶ በአጭር ግዜ በሀገር ውስጥም ሆነ አውሮፓና አሜሪካ ሰፊ እንቅስቃሴ ሲያደርግ የተበለጥን ሰይጣናዊ ስሜታቸው አገርሽቶ የከፈቱት ዘመቻም የሚረሳ አይመስለኝም፡፡(በአብዛኛው የሚዘምቱት ሀገራዊ ድርጅት ላይ ነው)

አንድነት የቅንጅት ወራሽ መሆኑና ( ቅንጅት የሚለው ስምና ሁለት ጣት ምልክት ወያኔዎችን ያባንናቸዋል)ከጅምሩ ያገኘው ተቀባይነት ያሰጋው ወያኔ ወ/ት ብርቱካንን ዳግም ሲያስር ለእነዚህ ሰዎች ፌሽታ ነበር፡፡አጋጣሚውን በመጠቀምም ቀሪዎቹን አመራሮች ከቅርብም ከሩቅም ወዳጅ መስለው በመቅረብ በምክርም በገንዘብም በሌላ ሌላውም ከወዲያ ወዲህ እያላጉ የት ይደርሳል የተባለውን አንድነት ሽባ አደረጉት፡፡ የእነርሱም የወያኔም ሴራ ተደማምሮ አንድነት አምስት አመት ሙሉ ታሞ በምርጫ 2007 ዋዜማ ግብአተ መሬቱ ተፈጸመ፡፡ እናቃብራችሁ አንኳን አላሉም፡፡

ማሳያ አምስት ሰማያዊ,- ይህኛውም ፓርቲ በ2004 ዓም ተመስርቶ በአጭር ግዜ በጠራው ሰላማዊ ሰልፍ  ለስድስት አመት የተዘጋን የሰላማዊ ሰልፍ ክልከላ በር አስከፈተ ተብሎ ስሙ ሲናኝ የሌላው መግነን የእኛን መኮስመን ያስከትላል የሚል ከይሲ አስተሳሰብ ያላቸው እነዚህ ወገኖች ዘመቻ የጀመሩት ከመቅጽበት ነው፡፡ ይሉት ቢያጡ  ሰበብ ቢቸግራቸው ከሌሎች ጋር ተባብሮ መስራት አለበት ብቻውን የትም አይደርስም አሉ፡፡ አልተሳካላቸውም እንጂ ይህን ሰበብ አድርገው በፓርቲው ውስጥ ክፍፍል እስከመፍጠር ደርሰውም እንደነበር ይታወቃል፡፡ሌላም ሌላም መጥቀስ ይቻላል፡፡አንድ ፓርቲ ጠንክሮ እንዳይወጣ ወይንም ፓርቲዎች ተባብረው በግንባርም ይሁን በውህደት ጠንክረው እንዳይታገሉ ካደረጉዋቸው ምክንያቶች አንዱ የእነዚህ ወገኖች ሴራ ነው፡፤

እነሆ አሁን ደግሞ የተለመደውንና መታወቂያቸው የሆነውን አፍራሽ ተግባር ጀመሩ፡፡  የኢሳይያስ ማንነትና የሻዕቢያ ምንነት የታያቸው ዛሬ ነው ? ጅብን ሲወጉ በአህያ ተከልሎ እንደሚባለው  ይህ ሰበብ ነው፡፡  ዋና አላማው ኢሳይያስንና ሻዕቢያን ከለላ አድርጎ በነጻነት ትግሉና ታጋዮቹ ላይ መዝመት ነው፡፡

ተቃውሞአቸው ምንድን ነው፡፡

የሚያነሱት ነገር ለክርክር እንዳይቀርብ ለመለስ ምትም አንዳይመች ተቃውሞአቸው ስልታዊ  መንገዳቸው የጎንዮሽ ነው፡፡የሚደግፉትም ሆነ የሚቃወሙት ነገር በግልጽ አይታወቅም፤ ዛሬ ያመሰገኑትን ነገ ይኮንኑታል፤ባከበሩ ማግስት ያዋርዳሉ፤ የእነርሱ የሆነ ሁሉ ቅዱስ በተቃራኒ የቆመ ወይም ለእነርሱ ያልተመቸ ሁሉ ርኩስ ነው፡፡ እነርሱ ሞክረውት አላስኬድ ባላቸው መንገድ ሌሎች መሄድ ከቻሉ በቅናት ያራሉ፡ እነርሱ ሊወዳጁት ያልቻሉትን ሰው ወይንም ድርጅት ሌሎች መወዳጀት ከቻሉ የውግዘት ናዳ ያወረዳሉ፤ እነርሱ ሞክረውት ያቃታቸውን ሌሎች ለማሳካት ከጀመሩ የማጥላላት ጥሩንባ ይነፋሉ፤ በታላቁ መጽኃፍ ትንቢተ ኢሳይያስ  ም፣48 ቁ.22 ላይ “ክፉዎች ሰላም የላቸውም” ተብሎ  እንደተጻፈው በክፋታቸው ለራሳቸው ሰላም አጥተው ሌላውንም ሰላም ያሳጣሉ፡፡

የሚሰሩትን አያውቁምና ይቅር በላቸው ተብሎ አንዳይተው፣ ዓላማችን ላሉት ስኬት አስበው ወቅት ጠብቀው የሚሰሩ መሆናቸውን አይተናል እያየንም ነው ፡፡ የተለመደ ተግባራቸው ነው ተብሎ ተንቆ አንዳይተው ብእራቸውም ሆነ ምላሳቸው የሚረጨው መርዝ ለትግሉ ውጤታማነት ሆነ ከድል በኋላ ለሚፈለገው መረጋጋት ብሎም  ለኢትዮጵያውን አንድነት ጠንቅ ነው፡፡ መፍትሄው  አላማችሁ ገብቶናል በቃችሁ ማለት መቻል ነው፡፡ይሄ ካልበገራቸውም ማንነታቸውን

Viewing all 15006 articles
Browse latest View live