Quantcast
Channel: Ethiopian News | ዘ-ሐበሻ | Latest News Provider | News For All
Viewing all 15006 articles
Browse latest View live

Hiber Radio: ፕ/ት ኦባማ ኢህአዴግና አማጽያኑን እንዲሸመግሉ መጠየቁ፣ አምንስቲ እንግሊዝ ለኢትዮጵያው አገዛዝ አፈና መጠንከርን ተጠቃሽ አደረገ፣ የአርበኞች ግንቦት ሰባት ጦርነት መክፈት የፈጠረው መነቃቃት፣ እስራኤላዊው ትውልደ ኢትዮጵያዊው በሐማስ እጅ መውደቅ የፈጠረው ተቃውሞ፣ የጋዜጠኛ ርዮት ዓለሙ እና ጋዜጠኛ ሰርካለም ፋሲል ቃለ መጠይቅ፣ የመን ሰንዓ ኤምባሲ ፊት ለፊት የወደቁ ኢትዮጵያውያን ያሉበት ስቃይ እና ሎሎችም

$
0
0
ጋዜጠኛ ሃብታሙ አሰፋ

ጋዜጠኛ ሃብታሙ አሰፋ

የህብር ሬዲዮ ሐምሌ 5 ቀን 2007 ፕሮግራም

<…የሌላው ሰው ህመም ህመማችን ሊሆን ይገባል። እንደ አሜሪካ ለሰብዓዊ መብት ያገባኛል የሚል መንግስት ያገባኛል ለሚለው ነገር መቆም አለበት ብዬ አስባለሁ…ዘርን ሀይማኖትን ያደረገ ክፍፍል ሳይኖር አንድ ላይ ለፍትሕ፣ለዕውነት ፣ ለዲሞክራሲ መቆም ብንችል ትልቅ ለውጥ ይመጣል። ዓለም አቀፉ ማህበረሰብም…> ጋዜጠኛ ርዮት ዓለሙ ከሰጠችን ቃለ መጠይቅ ላይ ከተናገረችው (ሙሉውን ያዳምጡት)

<…በሎስ አንጀለስ የተደረገው የአርበኞች ግንቦት ሰባት የገቢ ማሰባሰቢያ የተሳካ ነበር ። ያልተመቻቸው ሰዎች እንኳን አስቀድመው ትኬቱን በመግዛት እኛ ራሳችን ከጠበቅነው በላይ የተሳካ እንዲሆን…> አቶ ሳምሶን ደበበ በሎስ አንጀለስ የተደረገው ገቢ ማሰባሰቢያ አስተባባሪዎች አንዱ ከሰጡት ቃል የተወሰደ (ሙሉውን ያዳምጡ)

<…እስክንድር ከታሰረ አራት ዓመት ሊሞላው ሁለት ወር ብቻ ነው የቀረው። እስክንድር ብቻ ሳይሆን እስክንድር የታሰረለትም ዓላማ አብሮ ይፈታ …ፕ/ት ኦባማ በኢትዮጵያ የሚደረገውን ነገር አያውቁትም ብዬ አላስብም። ማነው ዓመታዊ ሪፖርት እያወጣ ሲያወግዝ የነበረው? ኦባማ አይደለም ኢትዮጵያ መሄድ ከፈለጉ … >

የጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ ባለቤት ጋዜጠኛ ሰርካለም ፋሲል ንግግር የተወሰደ ቀሪውን ያዳምጡት

< …እነዚህ ወገኖቻችን የመን የሚገኘው ኤምባሲ በር ላይ ወድቀው በረሃብ፣ በሙቀትና በዝናብ እየተሰቃዩ ነው። ዓለም አቀፉ የስደት ተመላሾች ማህበር(አይ.ኦ.ኤም) ካምፕ ወዳለበት ከሰንዓ ለመውጣት ፈቃድ ለማግኘት አማጽያኑን ስንጠይቅ ኢትዮጵያዊ መሆናቸውን አምጡ ተባልን። ሄደው ኤምባሲ ሲጠይቁ ከቀሩት ሁለቱ አንዱ ኢትጵአዊ መሆናቸውን አላረጋገጥንም ስላለ…ሁሉም ለነዚህ ወገኖቻችን ሊደርስ ይገባል..> ጋዜጠኛ ግሩም ተክለሃይማኖት በየመን ሰንዓ አገራችን እንገባለን ብለው በ<<ኢትዮጵያ>> ኤምባሲ በር ላይ እየተሰቃዩ ስላሉ ከሃምሳ የበለጡ ወገኖቻችን በተመለከተ ከተናገረው (ሙሉውን ያዳምጡት)

<…ጋዜጠኛ ሀብታሙ ምናለ ርዮት የተፈታች ዕለት ከቤቱ በደህንነቶች ታፍኖ ተወስዶ ዛሬ ግን ጣቢያ ይገኛል ፍርድ ቤት አልቀረበም…> ስለ ጋዜጠኛው መታፈን ምስክር ከተናገረው(ሙሉውን ያዳምጡ)

የደቡብ ሱዳን አራተኛ የነጻነት ቀኗ እና ሰላም የራቀው ውስጣዊ ሽኩቻ(ልዩ ዘገባ)

ሌሎችም

ዜናዎቻችን

ፕሬዝዳንት ኦባማ ኢህአዴግን ከተቃዋሚዎች ጋር እንዲሸመግሉ ጥሪ ቀረበ

አንዳንድ ባለስልጣናቱ በዕርቀ ሰላም አያምኑም ተባለ

አምንስቲ የኢትዮጵያው አገዛዝ ዜጎችን ለመሰለሉ እንግሊዝን ተጠቃሽ ሊያደርግ ይችላል አለ

የአርበኞች ግንቦት ሰባት ጥቃት መሰንዘር በሕዝቡ ውስጥ መነቃቃት እየፈጠረ ነው

የታክስ ጫናን በመቃወም በአዲስ አበባ ስጋ ነጋዴዎች የስራ ማቆም አድማ መቱ

የኢትዮጵያዊው ቤተ እስራኤላዊ በሐማስ እጅ መውደቅና ደብዛው መጥፋት በወገኖቹ ላይ ቅሬታ ፈጠረ

በወያኔ ላይ የተከፈተው ውጊያ ወደ አርማጭሆ መሸጋገሩን ግንባሩ ገለጸ

ኤርትራ የአፍሪካ ቀንድ የራስ ምታት ሳትሆን የፕሮፖጋንዳ ሰለባ መሆኗን ኢትዮጵያዊው ምሁር አውሮፓ ላይ ገለጹ

በውጭ የሚገኙ የነጻ ፕሬስ ጋዜጠኞች የቀሩትም ጋዜጠኞችና ጦማሪያን እንዲፈቱና ጸረ ሽብር ሕጉ እንዲሰረዝ ጠየቁ

ፌስ ቡክ የኢትዮጵያዊውን የግብረ ሰዶማዊ ድህረ ገጽ አካውንት መዝጋቱን አስታወቀ

<<ማንነቴን በመደበቄ ለፌስ ቡክ ሰለባ ሆኜያለሁ>> በአሜሪካ የሚኖረው ድህረ ገጹ የተዘጋበት ግለሰብ

ሌሎችም ዜናዎች አሉ


የሰላም ትግሉ በኢትዮጵያ (ክፍል ፫) አንዱዓለም ተፈራ –የእስከመቼ አዘጋጅ

$
0
0

 

ረቡዕ፤ ሰኔ ፲ ቀን፤ ፳ ፻ ፯ ዓመተ ምህቱረት ( 6/17/2015 )

የኢትዮጵያ ሰላማዊ ትግል አራማጆች፤ ከሌሎች ሰላማዊ ትግል አራማጆች የምንማረው

በክፍል አንድ፤ የሰላማዊ ትግሉ በአሁኑ ሰዓት በኢትዮጵያ ምን እንደሆነ ገልጫለሁ። በክፍል ሁለት ደግሞ፤ ስለሰላማዊ ትግሉ ያለንን ግንዛቤ አሳይቻለሁ። በዚሁ በሶስተኛው ክፍል ላይ፤ በኢትዮጵያ የሚካሄደው ሰላማዊ ትግል፤ ከሌሎች ከዚህ ቀደም የሰላማዊ ትግል ካካሄያዱ ሀገሮች የምንማረውን ተመክሮ እዘረዝራለሁ። ሰላማዊ ትግሉ፤ ዕለት በዕለት በገዥው ወገንተኛ አምባገነን ገዥ መንግሥት ፊት ኑሯቸውን በመምራት፤ በመንግሥታዊ መዋቅሩ ከተሰገሰጉት ካድሬዎች ጋር የሚላተሙ ኢትዮጵያዊያን፤ ትኩረታቸው ውስን ሆኖ፤ በጠባብ ጥያቄያቸው ዙሪያ ተጠምደው፤ በትምህርት ቤታቸው፣ በገበያ አዳራሻቸው፣ በእርሻ መስካቸው፣ በመሥሪያ ቤታቸው፣ በሚሠሩበት ፋብሪካ፣ በቀበሌያቸው፣ በገበሬ ማህበራቸው፣  ወታደሮች ለግዳጅ በተሰማሩበት ቦታ፤ ለኒሁ ውስን ጥያቄዎች መልስ ፍለጋ ሲሯሯጡ፤ በቦታው ተገኝቶ እኒህን ጥያቄዎቻቸውን ሀገራዊ ይዘት እንዲኖራቸው ማድረግ ነው። እኒህን ውስን የአካባቢ ጥያቄዎች፤ በሀገራዊ ራዕዩ ቦታ ሠጥቶ፤ መታገያ ዕሴቶች ሆነው፤ ሕዝባዊ መነሳሳት እንዲከተል ማድረግ ነው። የገዥው ክፍል እንዲህ ባለ በጉልበት የመግዛት ሂደት ሲሰማራ፣ ድህነት በሀገራችን በነገሠበት ወቅት፣ ሙስና በገዥው ክፍል ውስጥ ባህል ሆኖ ሲደራ፣ አድልዖ የዕድገት መሰላል በሆነበት አስተዳደር፣ ሕዝቡን በመርገጥ ግፉን ሲያበዛ፤ ሕዝቡ እምቢ ብሎ በሰላማዊ መንገድ ማመጹ፤ የሕልውና ጉዳይ ነው። ለዚህም ሕዝቡ እምቢተኛነትን ይዟል። ትክክለኛ ላልሆነ አሠራር ተባባሪ አልሆንም ብሏል። ሰላማዊ በሆነ እምቢተኝነት፤ የኅብረተሰቡን የፖለቲካም ሆነ የማንኛውም የአስተዳደር በደል ምንጭ አጥፍቶ፤ ትክክለኛ የሆነ ሥርዓት ለማምጣት ተነስቷል። እኒህ ሰላማዊ ታጋዮች፤ ሕዝቡን በማስተማር፣ ከፍተኛ ሕዝባዊ መዋቅር በመዘርጋትና ሕዝቡን በማነሳሳት፤ አጠቃላይ መሬት አንቀጥቃጭ ንቅናቄ ለማስከተል ቆርጠው ተነስተዋል። ታዲያ ከሌሎች የሰላማዊ ትግል ካካሄያዱ ሀገሮች፤ ምን ተመክሮ እንቀስማለን። ይህን ለመመለስ ነው ይህ ጽሑፍ የሚጥረው።

ሰላማዊ ትግል፤ በአመጽ ያለውን ገዥ ክፍል ለማስወገድ በመሰለፍና፤ ያለውን እንዳለ ተቀብሎ በመኖር መካከል ያለ የሕዝብ ይሄስ በቃ የማለት እርምጃ ነው። ያለውን ተቀብሎ ባለው ሥርዓት ሥር ለመኖር መወሰን አንድ ነገር ነው። ባንጻሩ ደግሞ፤ ያለውን ሥርዓት አውግዞ፤ ያንን ለመለወጥ ነፍጥ አንግቦ መነሳት ሌላው ነገር ነው። በመካከል ያለው ሰላማዊ ትግሉ ነው። ይህን ትግል፤ ከሕንድ እስከ አሜሪካ፣ ከፖላንድ እስከ ጓቴማላ፣ ከደቡብ አፍሪቃ እስከ በርማ፣ ከፊሊፒንስ እስከ ጀርመን፣ ከቻይና እስከ ቼዝ ድረስ፤ ታጋዮች አካሂደውታል። በርግጥ በቻይናና በበርማ ግፈኛ የሆኑ አምባገነን ገዥዎች፤ አረመኔነት በተመላበት መንገድ፤ የሕዝቡን አመጽ ለጊዜው አዘግይተውታል። እኛ፤ ከተሳኩትም ሆነ ካልተሳኩት የምንማረው አለ።

መሠረታዊ የሰላማዊ ትግሉ ማሽከርከሪያ፤ የገዥውን ክፍል ውስጣዊ ችግሮች በማባባስ፤ ቅራኔውና ውጥረቱ በታጋዩ ክፍልና በገዥው ክፍል መሆኑ ቀርቶ፤ በገዥው ውስጥ እንዲካረር በማድረግ፤ ግልብ ሆኖ እንዲፈረካከት መቦርቦር ነው። ጋንዲና ማርቲን ሉተር ኪንግ፤ የሰላማዊ ትግሉ አራማጆችና ባለስኬቶች ነበሩ። ከነዚህ አዛውንት ሰላማዊ ታጋዮች ብዙ የምንማረው ትምህርት አለ። ዋናው ቁምነገር፤ የነዚህን ግዙፍ ሰላማዊ ታጋዮች ግብር በማጥናት፤ ለኛ ሀገር ተስማሚ በሆነ መንገድ፤ ተመክሯቸውን መጠቀም ነው። እኛ በያዝነው ትግል፤ ዋና ገዥ ፍልስፍናችን ምንድን ነው? ሀገራችን ያለችበት አስጊ ሁኔታ የሚቀየረው፤ ሁላችን ታጋይና ለውጥ ፈላጊ ኢትዮጵያዊያን በአንድነት ተሰልፈን፤ በአንድ ራዕይና በአንድ ድርጅት ስንታገል ነው። ታግለን ደግሞ መመሥረት ያለበት፤ ሁላችንም የሚወክል የሽግግር መንግሥት ነው። ሰላማዊ ትግሉ፤ ያላማራጭ ባሁን ሰዓት ላለንበት የፖለቲካ ሀቅ፤ ብቸኛ መንገዱ ነው። ለምን?

አንድ ማዕከል ያለው ትግል ባገራችን በሌለበት ሁኔታ፤ የተለያዩ የኅብረተሰብ ክፍሎች በሞሉባት ኢትዮጵያ፣ በሃይማኖት፣ በቋንቋ፣ በትውልድ ሐረግ፣ በንብረት ብዛት፣ በአካባቢ ብልጽግናና በመሳሰሉት መለያያ መንገዶች ያለን መሆናችን አንዱ ምክንያት ነው። የተለያዩ የፖለቲካ ድርጅቶች፣ በተለይም የትውልድ ዘር ቆጠራ ላይ የተመሠረቱ የፖለቲካ ድርጅቶች የተስፋፉበት፣ የተለያዩ የትግል መስኮችና ግቦች የፖለቲካውን ምኅዳር ያጣበቡበት ሀቅ ሌላው ምክንያት ነው። አምባገነኑ ወገንተኛ ገዥ ተወግዶ፤ የነገዋ ኢትዮጵያ የሁላችን እንድትሆን አስተማማኝ የሆነ የትግል ስልት ማስፈለጉ፤ ሌላው ምክንያት ነው። ብዙ ታጋይ ኢትዮጵያዊያን ወደ ትግሉ፤ ለሌላው ሳይሆን ለራሳቸው ሲሉ መምጣታቸው፤ አስፈላጊና ወሳኝ ነው። ይህ ደግሞ ሌላው ምክንያት ነው። ባሁኑ ሰዓት፤ በገዥው ቡድን መካከል፤ መለስ ዜናዊን የመሰለ፤ ሁሉን ሥልጣን ጠቅልሎ በጁ የጨበጠ አንድ አምባገነን በሌለበት ወቅትና፤ እያንዳንዳቸው የራሳቸውን ወገን ለማጠናከር በሚሯሯጡበት ሰዓት፤ በመካከላቸው ያለውን ክፍተት ለማስፋትና ጥርጣሬ እንዲገባባቸው ለማድረግ፤ ግፊት ከሕዝቡ ያስፈልጋል። ሰላማዊ ትግሉ ከላይ ከተዘረዘሩት በተጨማሪ፤ ለዚህ የገዥው ተጨባጭ እውነታ፤ አጣዳፊና ተግባራዊ መደረግ ያለበት ግዴታ ነው። ባሁኑ ሰዓት በታጠቀ ኃይል ከመፈረካከታቸው ይልቅ፤ በመካከላቸው በሚፈጠረው ቅራኔና ሽኩቻ፤ የበለጠ መዳከማቸው አመኔታ አለው። እናም ይሄን ለማባባስ አንድ የሚያደርጋቸውን ሳይሆን የሚሰነጣጥቃቸውን መምረጥ አለብን። እናም ሰላማዊ ትግሉ ይሄን ለማድረግ ይረዳናል። የሱማሌና የዩጎዝላቪያ ሀቅ፤ በላያችን ላይ ከብዶ ሊያንዣብብ ያስፈልጋል።

በርግጥ ሰላማዊ ትግሉን መምረጥ ማለት፤ የማህተማ ጋንዲን ወይንም የማርቲን ሉተር ኪንግን ተግባር በቀጥታ መቅዳት ማለት አይደለም። የኛ ሀገር የፖለቲካ ሁኔታና ያለው ተጨባጭ ሀቅ ገዥ ነው። ለጋንዲና ለማርቲን የሃይማኖት መሠረት ዋና ትክላቸው ነበር። በርግጥ ኢትዮጵያዊያን፤ ሃይማኖተኞች ነን። በክርስትያንም ሆን በእስልምና ተከታዮች ዘንድ፤ ለሌሎች ጠበቃ ሆኖ መቆምና ግፍን መቃወም ባህላችን ነው። ሰላምታ አለዋወጣችን እንኳ፤ አንገታችንን ዝቅ አድርገን በመድፋት፤ ሰላምታ ከምንለዋወጠው ሰው ራሳችንን አሳንሰን ነው። አስደጋጭ ሁኔታ ሰፈጠር፤ ለፀሎት ወደ ቤተ ክርስትያንና ወደ መስጂድ መሮጣችን እውቅ ነው። አብሮ ለጸሎት ወደ ቤተ እመነት መሄድና አብሮ መጸለይ የተለመደ ነው። እንግዲህ ይህ ብዙ የሚያመሳስለን ሁኔታ መኖሩን ይመሰክራል። ለነሱ ዋናው እምነታቸው፤ ገዥውን ክፍል ተገዥ ለማድረግ ሳይሆን፤ ሁሉም እኩል የሚሆንበት የወደፊት እንዲፈጠር ማድረግ ነው። ይሄ በቅኝ ግዛት ትማቅቅ ለነበረችው ሕንድ፤ ምን ያህል እንደሠራ ማየቱ ቸግሮኛል። እንግሊዞች ወጥተው ሕንዶች የራሳቸው መንግሥት እንዲመሠርቱ የታገለው ጋንዲ፣ ይሄን መስበኩ ለኔ ገርሞኛል። ባንጻሩ ማርቲን ምርጫ አልነበረውም። ኔልሰን ማንዴላም ቢሆን ምርጫ ስላልነበረው፤ በአውሮፓውያንና አሜሪካውያን፤ ለውጡ ዘምዶቻቸውን እንደማይጎዳና ጥቁሮቹን ባሉበት የድህነት ሰቆቃ እንዲማቅቁ መደረጉን ተገዶ ተቀብሏል። ወራሪንና እንደወራሪ የሚገዛን ቡድን፤ አስተናግዶ እኩል ለማድረግ፤ የሀገራችን ሀቅ አያመችም።

ሌሎች ጠቃሚ የሆኑ ትምህርቶች አሉ። ሰላማዊ ትግሉ መማርና መመራመርን መጠየቁን ያምኑበት ነበር። ለነሱ እውነተኛ እውቀት ማለት፤ በቦታው በተጨባጭ ያለውን ሀቅ ተገንዝቦ፤ ሂደቱን በማስላት፤ ተለዋዋጭ ሁኔታዎችን በማካተት፤ ወደ መሠረታዊ ዋና ግቡ መጓዝ ማለት ነበር። ደጋግሞ ስለሰላማዊ ትግሉ ምንነት መስበክና ማስተማር የመሪዎቹ ኃላፊነት መሆኑን አስምረውበታል። የሰላማዊ ትግሉ በተግባር ላይ ስለመዋሉ እውነተኛነት፤ ጽኑ እምነትና ቆራጥነት ግድ ነበሩ። በጋጠ ወጦችና በገዥው ታጣቂዎች ለደረሰባቸው ጉጥጫና ግፍ፤ የአካል፣ የመንፈስና የንብረት ጥቃት፤ መልሳቸው ግልጽ ነበር። “ያነገትኩት እውነት፤ ክቡርና ጠንካራ ስለሆነ፤ ውሎ አድሮ፤ አቸናፊ ነኝ!” ነበር። የዚህ ትግል መሪዎች፤ የአእምሮ ነፃነት ያላቸውና ለግል ተጠቃሚነት ቦታ ያልሠጡ መሆን አለባቸው ብለዋል። በሰላማዊ ትግል የሕዝቡን የለውጥ ፍላጎት ማሟላት፤ ትክክለኛ ተግባር ነው ብለው አምነዋል። ከማንኛውም ቦታ የሚመጡ የተለያዩ ሃሳቦችን ለማዳመጥና ለማመዛዘን ፈቃደኞች ነበሩ። የሰላማዊ ትግሉ ሂደት፤ ለኅብረተሰቡ ኑሮ፤ መሠረታዊ ለውጥ ማምጣት ነው። እናም ከትግሉ ስኬት በኋላም አገልጋይ የሚሆኑ ባህሪና ጥበቦችን በሥልጠናና በተግባራዊ ልምድ ማዳበር ይጠቅማል። ለሚከተለው ሰላምና ብልጽግና፤ በተለይም ከጦርነት እሽክርክሪት ለመውጣት መሠረት ነው። እብሪትና ድንቁርና፤ ጦር ወደ መምዘዝና ካንተ መቼ አንሼ ወደሚል ያመራሉ።

የሕዝቡ የነፃነት ፍላጎት አይሎ፤ በየቦታው እምቢተኝነቱን ሲያሰማ፤ የገዥው ወገንተኛ አምባገነን መንግሥት ሁለት ምርጫ ብቻ ከፊቱ ይደቀናሉ። እኒህ ወሳኝ የሆኑ ምርጫዎች፤ የገዥውን ቡድን አረመኔያዊ ግፍ፣ የሕዝቡን አጸፋ አመላለስና የወደፊቱን የሀገራችን ሕልውና ይወስናሉ። የመጀመሪያው ለሕዝቡ እምቢተኝነት ተገዝቶ፤ የሕዝቡን ፍላጎት ለሟሟላት እሽ ማለት ነው። ሁለተኛው፤ በእብሪት ተሞልቶና እኔ ገዢ ነኝ፤ እኔ ብቻ ያልኩት መፈጸም አለበት በማለት፤ ጉልበቱን ተጠቅሞ የሕዝቡን እምቢተኝነት በጭካኔ ለመቅጨት ሠይፉን ከአፎቱ መምዘዝ ነው። የመጀመሪያው እንደሂደቱ የሚመለስ ሲሆን፤ የአምባገነኖች መጨረሻ እንዳስገነዘበን ግን፤ በአብዛኛዎቹ ቦታዎች፤ የሁለተኛው ምርጫ ነው የተለመደው። የሕዝቡ የአጸፋ መልስ፤ የገዥውን የእብሪት ጉልበት መቋቋምና የበላይነቱን መውሰድ ይጋብዛል። ያኔ የሕልውና ግዴታ ቦታውን ይወስዳል። በመኖርና ባለመኖር መካከል የሚቀመጥ መርጫ፤ በማናቸውም መንገድ መኖርን ይዞ መነሳቱ፤ አጠያያቂ አይደለም።

በአራተኛው ክፍል፤ ከየት እንጀምር የሚለውን ተግባራዊ ጉዳይ ይዞ ይቀርባል።

eskemecheeske.meche@yahoo.com  http://nigatu.wordpress.com

ለመሆኑ ጋዜጠኛ አለምነህ ዋሴ ማን ነዉ? የሕይወት ታሪኮቹና የፍቅር ሕይወቱ ምን ይመስል ይሆን?

$
0
0


ለመሆኑ ጋዜጠኛ አለምነህ ዋሴ ማን ነዉ? የሕይወት ታሪኮቹና የፍቅር ሕይወቱ ምን ይመስል ይሆን?
ለመሆኑ ጋዜጠኛ አለምነህ ዋሴ ማን ነዉ? የሕይወት ታሪኮቹና የፍቅር ሕይወቱ ምን ይመስል ይሆን?
Zehabesha.com

5ኛው የመድረክ አባል ተገደለ

$
0
0

medrekመድረክ ባወጣው መግለጫ ከ2007 ምርጫ በሁዋላ ማንነታቸው ባልታወቁ ሰዎች የተገደሉ የመድረክ አባላት ቁጥር 5 ደርሷል። የኢህአዴግ አገዛዝ በደቡብና ኦሮምያ የሚፈጽማቸው ድብደባዎችና እስራቶች መጨመራቸውንም መድረክ ገልጿል።
በከፋ ዞን በግንቦ ወረዳ በአድዮ ካካ ምርጫ ክልል በጎጀብ ምርጫ ጣቢያ የመድረክ ምርጫ ታዛቢ/ወኪል ሆነው የሠሩት አቶ አሥራት ኃይሌ ማንነታቸው ባልታወቁ ሰዎች ቅዳሜ ሰኔ 27 ቀን በተፈጸመባቸው አሰቃቂ ድብደባ ምክንያት ሕይወታቸው ማለፉን የገለጸው መድረክ፣ ድብደባው የተፈጸመው ጎረቤቶቻቸውና ቤተሰባቸው ወደ ገበያ ሄደው በነበረበት ወቅት ነው።
አቶ አስራት ቦንጋ ከተማ 01 ቀበሌ በሚገኘው መኖሪያ ቤታቸው ውስጥ ብቻቸውን እያሉ ከረፋዱ በ4፡00 ሰዓት ላይ ወደ ቤታቸው በመጡና ለጊዜው ማንነታቸው በትክክል ተለይቶ ባልታወቁ ሰዎች ጭንቅላታቸውን ተመትተው ራሳቸውን ከሳቱ በኋላ በተለያዩ የሰውነት አካሎቻቸው ላይ ዘግናኝ ድብደባ ተፈጽሞባቸዋል። አቶ አስራት ወደ ጅማ ሆስፒታል ተወስደው በመታከም ላይ እያሉ ሰኔ 29 ቀን 2007 ዓ ም ህይወታቸው ማለፉን መድረክ ገልጿል።
የቃለሕይወት ቤተክርስቲያን እምነት ተከታይ የሆኑት የአቶ አሥራት፣ ሰኔ 30 ቀን ወደ መኖሪያቸው ቦንጋ ከተማ አስከሬናቸው የተመለሰ በሆንም፣ የቤተክርስያኑ አባላት ሲቀበሩ በቆዩበት የቀብር ቦታ ላይ የቀብር ሥነሥርዓታቸው እንዳይፈጸም ከኃላፊነታቸው ውጭ በጉዳዩ ጣልቃ በገቡትና የካፋ ዞን አስተዳዳሪ የአቶ አስራት መኩሪያ ወንድምና በከተማው የኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ኃላፊ የሆኑት ቄስ መምህር ታፈሰ መኩሪያና በግንቦ ወረዳ ባለሥልጣናትና ፖሊሶች ተከልክሎ መቆየቱን ገልጿል።
ይሁን እንጅ ሕዝቡ ባቀረበው አቤቱታ ረቡዕ ሃምሌ 1 ቀን 2007 ዓ ም የሟቹ አስከሬን መቀበሩን መድረክ አክሎ አስታውቋል።
በካፋ ዞን የመድረክ ተወካይ የሆኑት አቶ አድማሱ አምቦና ሌሎች የዞኑ የፓርቲው አመራር አባላት ሁኔታውን ተከታትለው መረጃ እንዳያስተላልፉ በቢሮ ውስጥ እያሉ ከቢሮአቸው እንዳይወጡ ቢሮው በወታደርና በታጣቂዎች ተከቦ መቆየቱንና ስለሟቹ ማንነትና ስለግዲያው ሁኔታ የማጣራት ሥራ ለማከናወን የተቻለውም የቀብር ሥነሥርዓቱ ተፈጽሞ በመድረክ ጽ/ቤት ላይ ተደርጎ የነበረው ከበባ ከቆመ በሁዋላ መሆኑን ደርጅቱ አስታውቋል።
በኦሮሚያ በሁለት አባላት፣ በትግራይ በአንድ አባል እናንዲሁም በደቡብ በአንድ አባል ላይ ተማሳሳይ ግዲያዎች መፈጸማቸውን የፖለቲካ ድርጀቱ አስታውሷል።
በዚሁ ዞን በፈለገሰላም ወረዳ በጨታ ምርጫ ክልል በቦባ ቀበሌ የመድረክ የምርጫ ታዛቢ ወኪል የነበሩት አቶ ገረመው ቆዲ፣ የምርጫው ቀስቃሾች የነበሩት አቶ አሥራት ሻውአኖ፣ አቶ ገረመው ጋንአቾ እና የሾላይ ቀበሌ ታዛቢ ወኪል የነበሩት አቶ ገዛሃኝ ገንቢ እንደዚሁም በዴቻ ወረዳ ጭሪ ምርጫ ክልል የሚታ ቀበሌ ታዛቢ ወኪል የነበሩት አቶ ተክሌ ቆጭቶ ከሚያስፈሊጋቸውና ከአቅማቸው በላይ የሆነ ማዳበሪያ እንዲገዙ በቀበሌው አመራሮች ታዘው ትዕዛዙን ለመፈጸም ባለመቻላቸው ተይዘው እንዲደበደቡና እንዲታሰሩ ተደርጓል።
በቤንች ማጂ ዞን ሸዋ ቤንች ወረዳ ደግሞ አቶ መኮንን ሚቱስ፣ አቶ ማሙር ሁሌት፣ አቶ ሉቃስ አለሙ፣ አቶ ቶሳ ሳቁያብ፣ አቶ ዘለቀ ታቹያብ፣ አቶ ሐሰን ዴሪያብ፣ አቶ ተስፋዬ ወ/የስ፣ አቶ ሳሙኤል ቸሪቲ፣ አቶ መላኩ ታርሳ፣ አቶ መንግስተ ሾዳ፣ አቶ ኬሪቲ ቡጢያብ፣ አቶ አድነው ወ/የስ እና አቶ አብርሃም ሳሙኤል የሚባሉ የመድረክ አባላት መስከረም ሲሲ በሚባል ቀበሌ ውስጥ ባለው ፖሊስ ጣቢያ ከአራት ቀን እስከ ሁለት ሳምንታት ያህል ጊዜ ታስረው ከቆዩ በኃላ ተለቀዋል፡፡ ባሎቻቸው እቤት ውስጥ ያልተገኙ 12 ሚስቶች ታስረው ከቆዩ በኃላ እንደተፈቱ ፓርቲው አስታውቋል።
በሸኮ ልዩ ወረዳ የፉዥቃ ቀበሌ ነዋሪና የመድረክ የምርጫ ታዛቢ የነበሩት አቶ ደርጀር ዲኩ እና አቶ ፀጋዬ ፉርጃ በወረዳው ፖሊስ ጣቢያ ታስረው ይገኛሉ። ደቡብ ኦሞ ዞን በማሊ ወረዳም እንዲሁ አቶ ታገሰ ቡርዝጋ፣ አቶ ቦት ቦርታ እና አቶ ነጌ ደምቤ የሚባሉ የመድረክ አባላት ለመድረክ ቅስቀሳ አካሄዳችሁ ነበር በሚል ውንጀላ ታስረዋል፡፡
በዚሁ ወረዳ የኩንታር ቀበሌ ነዋሪ የሆኑ 26 አርሶ አደሮች የመድረክ ደጋፊና ቀስቃሾች ስለነበራችሁ የእርሻ መሬታችሁን ልቀቁ በመባላቸው በቀበሌው አመራር አባላት የእርሻ መሬታቸውን ተነጥቀዋል፡፡
በጋሞጎፋ ዞን በካምባ ወረዳ ደግሞ በመድረክ በኩል በምርጫው ወቅት የምርጫ ጣቢያ ወኪል/ታዛቢዎች ሆነው የሠሩት አቶ ግዛ ግብሳ እና አቶ ገጦሬ ገባሌ የተባሉ የግብርና ኤክስተንሽን ሠራተኞች ከሚያዚያ ወር 2007 ጀምሮ ከሥራና ከደመወዛቸው
የታገዱ ሲሆን፣ አቶ ሕዝቃኤል ፋንጌ እና መምህር አቴ አይሳ የተባሉት የመድረክ የክልል ም/ቤት ዕጩ ተወዳዳሪዎች ደግሞ የየካቲት ወርና ከሚያዚያ ወር 2007 ጀምሮ እስከአሁን ድረስ ያለው ደመወዛቸው በሥራ ላይ እያሉ ታግዶ ይገኛል፡፡
በወረደው ውስጥ ለጊዜው ቁጥራቸው ያልታወቁ በርካታ የመድረክ አባላትና ደጋፊ የሆኑ አርሶ አደሮችም ከአቅማቸው በላይ እንዲገዙ የተመደበባቸውን ማዳበሪያ በወቅቱ አልገዙም በሚል ሰበብ እስከ 1000 ብር የሚደርስ የገንዘብ ቅጣት እየተጣለባቸው እንዲከፍሉ ተገደዋል ሲል ፓርቲው አስታውቋል።
በኦሮሚያ በጉጂ ዞን ዋመና ወረዳ አቶ ሮባ ገልቹ፣ በቦረና ዞን መልካ ሶዳ ወረዳ አቶ ጠደቻ አሬሮ፣ በምስረቅ ሻዋ ዞን ሞጆ ወረዳ አቶ ዝናቡ ዳምጤ የሚባሉ የኦፌኮ/መድረክ አባላት በየወረዳዎቻቸው ላለፉት ሁለት ሳምንታት ታስረው ይገኛሉ፡፡
በምሥራቅ ሸዋ ዞን ቦሰት ወረዳ ደግሞ አቶ አሸናፊ ነጋሽ፣ አቶ ለሚ እንዳለማው፣ አቶ ባብሣ ገመዳ፣ አቶ ጉዳታ ቢራ፣ ወ/ሮ ወይንሸት፣ አቶ እሸቱ ዲማ፣ አቶ አንበሳ ያኢ፣ አቶ ታምሩ ቁምቢ፣ አቶ ቀነኒ ደሜ እና ወ/ሮ ደምበልቱ ዳሜ የተባሉ የመደረክ አባላትና ደጋፊዎች የሆኑ 10 አርሶ አደሮች መኖሪያ ቤቶች በቀበሌው አመራሮች እንዲፈርሱ ተደርጓል፡፡ በምዕራብ ሸዋ ግንደበረት ወረዳ የኦፌኮ መድረክ አደራጅና በምርጫው ወቅት የመድረክ ቀስቃሽና ተዘዋዋሪ ታዛቢ የነበረው ተማሪ ጉቱ ሦሬም በምርጫው ቅስቀሳ ወቅት ያልተፈቀደ ስብሰባ አካሄደሃል በሚል መሠረተብቢ ክስ በጸጥታ ኃይሎች ተደብድቦ ታሥሮ እንደሚገኝ ፓርቲው የላከው መግለጫ ያመለክታል።
ከምርጫ 2007 በሁዋላ የተገደሉ የተቃዋሚ ድርጅት አባላት 6 ደርሷል።

Source:: Ethsat

አንዱዋለም አራጌ ለልጁ የጻፈው –የሚሊዮኖች ድምጽ

$
0
0


Andualem f
ሁለት ሕጻናት  አሉት። የመጀመሪያ ወንድ ልጁ ሩህ ይባላል። ከአራት አመታት በፊት፣ ልጁን ከትምህርት ቤት ሊያወጣ ወደዚያ ሲያመራ ታጣቂዎች ከበቡት። እየሰደቡ፣ እየደበደቡ ወደ ወህኒ ወሰዱት። አንድ ፖሊስ ይበቃ ነበር። ግን የለየለት ነፈሰ ገዳይ የሚይዙ ይመስል፣  ይሄን አንድ ሰላማዊ የልጅ አባት ለመያዝ ተረባረቡ። አይ ጭካኔ !

ይህ ሰው አንዱዋለም አራጌ ነው። የአንድነት ፓርቲ ምክትል ፕሬዘዳነት የነበረ፣ አንጋፋ ወጣት ፖለቲከኛ። ባላጠፋው ጥፋት፣ ለሰላም በቆመ፣ በዉሸት ክስ፣ ሽብርተኛ ተብሎ የእድሜ ልክ  እስራት የተፈረደበት።

ልጅ ሩህ ከዚያ ቀን ጀምሮ ከአባቱ ጋር አላደረም። አባቱ ለአገርና ለሕዝብ ሲል ወህኒ ወረደ። አገር ትጠቀም ተብሎ ልጅ ሩህ አባት ተነፈገ።  አገር ልጥቀም ብሎ እንዱዋለም አራጌ፣ እንደ  ሌሎች አባቶች ልጆቹን የማሳደግ እድል ተነፈገ። ለአገርና ለሕዝብ በመቆሙ፣ የአገርን የሕዝብ ጥቅምን በማስቀደሙ የጨካኞ በትር አረፈበት። ይህ የኢትዮጵያ ኔልሰን  ማንዴላ የሆነው  አንዱዋለም አራጌ !!!!!

አንዱዋለም አራጌ፣  አልጋ ዳር ሆኖ ከልጆቹ ጋር መጫወት፣ ለነርሱ ተረት ማውራት፣ የልጆች መጽሃፍ ማንበብ አልቻለም። ግን በመንፈስ ከነርሱ ጋር ነው የሚያድረው። ያለዉን ፍቅርና ናፍቆት ከቃሊቲ በጽሁፍ ይገልጻል። ለወንድ ልጁ ሩህ  አንድዋለም ሲጽፍ “ከዘላለም በፊት የተቸርከኝ  …እንኳን ወለድኩህ” ይላል። “የአምባብገነኖች ግፍ ሰለባ” ይለዋል፤ አገዛዙ በዉሸት ክስና  በግፍ ዜጎችን በሚያስረበት  ጊዜ የሚጎዱት ልጆች፣ ቤተሰብም እንደሆነ ለማሣየት።

አንዱዋለም አራጌ ከሚወዳቸው ልጆቹ መለየቱ ትልቅ ሕመም እንደሆነበት ደብዳቤው ያሳያል። ሆኖም አንዱዋለም እርሱ የኖረባት በግፍ የተሞላች፣ በዘረኝነት የተከፋፈለች ኢትዮጵያን ለልጆቹ ማስረከብ አልፈለገም። እርሱ መስዋትነት ከፍሎ ልጆቹና የየልጅ ልጆቹ በነጻነት እንዲኖሩ ይህ ወያኔዎች “ሽብርተኛ”  የሚሉት ምመላአው የኢትዮጵያ ህዝብ ግን እንደ ጀግና የሚያየው ወጣት የአንድነት መሪ በጨካኖች በትር ስቃይ እየደረሰበት ነው።

 

ከዋክብትና ብርሃናት ሰማያትና አለማት

በፈጣሪ ቃል ከመፌጥራቸው በፊት

በዚያ በፈጣሪ እቅፍ በዚያ በኔ ጉልበት ዉስጥ

ከስጋና ደሜ ተዋህደህ

ከነፍሴ ደም ስሮች ጋር ተገምደህ

በልቤ ጓዳ ዉስጥ ተኝተህ ሳለህ የማውቅህ

ከዘላለም ዘመናት በፊት የተቸርከኝ

ከዘላለም ዘመናት በፊት የወለድኩህ

በድቅድቅ ዉስጥ ያገኝሁህ

የነፍስያዬ ሃቅል ሩህ

የሕይወቴ የብርሃን ጎርፍ

የሕይወቴ ምገስ ካባ

የፌሽታዬ ምንም ቀዘባ

የአምባገነኖችን ግፍ ሰለባ

የአብይተነታቸው ማሳያ ጫማ

በውል የማታወቀው እስረኛ አባት ጠያቂ

ያለተመለሱ ጥያቄዎች ማህደር አማቂ

የነፍስዬ ሃቅል ሩህ በድቅድቅ ዉስጥ ያገኘሁህ

የሕይወቴ የብርሃን ጎርፍ

እንኳን ወደዚህ አለም መጣህ

እንኳን በድጋሚ ወለድኩህ

 

———-//—————–

እኔና ስርጉተ–  አልተግባብቶም        ይገረም አለሙ

$
0
0

በቅድሚያ እህቴ ስርጉተ ለአስተያየትሽ አመሰግናለሁ፡፡ ሁለት ገጽ ጽሁፌ እያንገሸገሽሽ አንብበሽ በተረዳሽውና በገባሽ መልክ  በጨዋ አቀራረብ አስተያየት በመስጠትሽ፤- እኛ ኢትዮጵያውያን በእጅጉ ከሚጎድሉን በርካታ ነገሮች አንዱ ይህ ነው፤ በጽሞና መነጋገር ሀሳብ መለዋወጥ መደማመጥ አለመቻል፡፡ ሀሳብን በሀሳብ ከመሞገት ይልቅ ፈጥኖ ዘለፋና ፍረጃ፤

እህቴ  በጽሁፏ መጀመሪያ ሀይለ ቃሏን ብቻ አውጥቼ ጠረጴዛየ ላይ አድርጌ ፈተሸኳት ስትል በጥሞና አንብባዋለች በሚገባም  ተረድታኛለች የሚል ስሜት አድሮብኝ ነበር፡፡ ነገር ግን 6 ገጽ የፈጀውን ሀሳቧን አንብቤ ስጨርስ እንደገባኝ ሀይለ ቃል ብላ ያወጣቻቸውን ብቻ ይዛ  በእነኛ ላይ ተመስርታ አቶ ገብሩ አስራትን እያሰበች (ርሷ እንዳለችው) ሌላውን የጽሁፉን መልእክት በትኩረት ባለማየቷ  ያነበበችው በሀሳቧ ታወጣ ታወርድ ከነበረው  የተምታታባት ይመስላል፡፡ ይህም በመሆኑ ጽሁፉ የማይለውን ትርጉም በመስጠት በሀሳብ ሳንለያይ ተለያየን፤ አንድ ቋንቋ እየተናገርን ሳንግባባ ቀረን፡፡

በሀሳብ መግባባት ሲቻል መልካም ነው፡፡ ካልሆነ ደግሞ ላለመግባባትም መግባባት ጥሩ ነው፡፡ አንድ አይነት ሀሳብ እያንጸባረቁ አለመግባባት ያለመደማመጥ ውጤት በመሆኑ ምን አልባት ሀሳቤን በትትክል አልገለጽሁ ይሆን እንዴ ብዬ ጽሁፌን እንደገና አነበብኩት፡፡ ግና ስርጉተ የፈንጅ ያህል ነው ያቆሰለኝ ያለችውን ትርጉም የሚሰጥ ቃልም ሆነ አረፍተ ነገር ማግኘት አልቻልኩም፡፡ እናም ሲሆን ለመግባባት ከልቻልንም ላለመግባባት መግባባት መደማመጡ መልካም ነውና ከረዥሙ ጽሁፍ ትንሽ ማሳያዎችን በመጥቀስ  ሀሳቤን ግልጽ ለማድረግ ልሞክር፡፡

1-„የልማታዊ መንግሥትበለው! ይህም በራሱ አቅሙአይደለም። ያለማው አካባቢ ካለ ጥብቅናይቆምለት። ምን አልባት ብላለች ስርጉተ፡ ይህ ብቻውን የእኔ ጽሁፍና ስርጉተ እንዳልተገናኙ በቂ ማሳያ ነው፡፡ ምንም ማብራሪያ ሳያስፈልግ በጽሁፌ የገለጽኩትንና ይህን ለማለት ያበቃትን ዐ.ነገር  ደግሜ ላስፍረው፤ “አሁን ልማታዊ መንግሥት እያለ ራሱን እየጠራ ነው ታዲያ እኛ በዚህ  እንጠራዋለን?” ነው የሚለው የእኔ ጽሁፍ፡፡ ለራሱ በሰጠው ግብሩን በማይገልጽ መጠሪያ ልንጠራው አይገባም እያልኩ ስርጉተ ያለማው አካባቢ ካለ ጥብቅና ይቆምለት በማለት ልማታዊ መንግሥት ተብሎ ይጠራ እንዳልኩ አድርጋ ነው የተረዳችው፡፡

2-እኔ እርስዎ የጻፉት ጹሑፍ የፈንጅ ያህል ነውያቆሰለኝ። አይደለምሌላውን። እያቅለሸለሸኝ ነውያነበብኩት፤ ስለምን? በአጋጣሚዎች ምክንያት ብዙ ነገሮችን በጥልቀት ስለማዳምጣቸው በማለት እኔ ወያኔ በኢትዮጵያና በኢትዮጵያውያን ላይ ያደረሰውን በደልና ጥፋት እንደማላውቅ ወይንም ወደ ጎን አድርጌ በደጋፊነት አንደተሰለፍኩ ገምታኛለች፡፡ ጽሁፌ ውስጥ የትኛው አገላለጽ ይህን ትርጉም እንደሰጣት አልገባኝም፡፡ ብታሳየኝ ጥሩ ነበር፡፡

ስርጉተ በሰፊው የገለጸችውን የሰው ልጅ ሊሰራው የማይገባ እርኩስ የሆነ የወያኔ ተግባር አውቃለሁ፡፡ የማውቀው ደግሞ  በስማ በለው ሳይሆን እየኖርኩበት በራሴ ጭምር ደርሶም እየደረሰም ነው፡፡ ማወቅ ብቻ ማውገዝ ብቻ አይደለም ስልጣን ጨብጦ የጫካ ርኩስ ተግባሩን ከቤተ መንግሥት ሆኖ መፈጸም ከጀመረበት ግዜ አንስቶ ከሰላማዊ ታጋዮች ጋር ተሰልፌ የታገልኩ ነኝ፡፡እናም በወያኔ ማንነት ምንነትና እንዴትነት ላይ ልዩነት ሳይኖረን ነው ያልተግባባነው፡፡

3- የነገ ኢትዮጵያ መከራው በቁርሾ እንዳይወራረድ በመቻቻል እንዲሰክንእንሻለን። ይህ የስርጉተ አባባል የእምነቴ መሰረት በጽሁፌ የተገለጸው ሀሳቤም ማጠንጠኛ ነው፡፡ ለዚህም ነው አልተግባብቶም ለማለት የበቃሁት፡፡ትግሉ ወያኔን ማሸነፍ ብቻ ሳይሆን ከወያኔ በኋላ ልጆቿ በፍቅር በሰላም በእኩልነትና በነጻነት የሚኖሩባት ኢትዮጵያን እውን ማድረግ ከሆነ ዛሬ የምንናገረው የምንጽፈውም ሆነ ተግባራዊ የምናደርገው ይህን ያነዘበ መሆን አለበት፡፡ እናም ስርጉተ እንዳልሽው የነገ ኢትዮጵያ መከራው በቁርሾ እንዳይወራረድ በመቻቻል እንዲሰክን ከመሻት ባለፈ እውን እንዲሆን  ከተመኘን ወያኔና ትግረኛ ተናጋሪ ወገናችንን ለያይቶ ማየት  ይበጃል፡፡

4 በዘመነ ወያኔ ሃርነት ትግራይ ነፃ ውጪ አስተዳደር እያንዳንዱ የእንቅስቃሴ ነጥብ በመርዝ የተበከለ ስለሆነ ሌላ የሰከነ የመንፈስ አብዮት የሚጠይቅ ተግባር ከፊት ለፊት ብሄራዊ ነፃነት ፈላጊውን ህዝብይጠብቀዋል። ወንድሜ ሆይይህ የሚጎረብጠዎት ከሆነ…….

የእኔኑ ሀሳብ የደገመ ሀሳብ እንደምን ይጎረብጠኛል፡፡ ወያኔን የትግሬ ነጻ አውጪ ማለት የሱን መርዝ ማራባት ነው፤ ምክንያቱም አንድም እሱ ሥልጣን ፈላጊ አንጂ ነጻ አውጪ ስላልሆነ፡ ሁለትም አባባሉ ትግረኛ ተናጋሪ ወገናችንን በሙሉ ጠቅሎ ከወያኔ ጋር በአንድ ቅርጫት የሚያስገባና ሌላው ኢትዮጵያዊ ትግረኛ ተናጋሪውን ወገን አንደሚጠላ አድርጎ በመስበክ የርሱ ጋሻና ዋሻ ለማድረግ የሚሰራውን ሴራ ማገዝ የሚረጨውን መርዝ ማሰራጨት ነው የሚል እምነት አለኝ፡፡ፈጣሪ ነብሳቸውን እንዳሻው ያድርጋትና አቶ መለስ መቀሌ ተኝተው በትግረኛ ቋንቋ “እኛ ከሥልጣን ብንወርድ ነፍጠኞች አንድ ቀን አያሳድሩዋችሁም” በማለት የረጩት መርዝ በምንም ምልኩ አላማቸውን አንዲያሳካ እኛ በማወቅም ይሁን በበደል ግፊት ተባባሪ መሆን የለብንም ነው የእኔ ጽሁፍ መልእክቱ፡፡ እርሱ በጥላቻ መርዝ የበከለውን እኛ በፍቅር እናጽዳው ነው፡፡ወያኔ ለሥልጣኑ እድሜ ሲል ለሚፈጥረው መለያየት እኛ በር አንክፈት መንገድ አንስጥ ነው፤እሱ ጎሰኝነትን ሲያቀነቅን እኛ ኢትዮጵያዊነትን እንዘምር ነው ሀሳቤ፡፡

4በሌላ በኩል ተበድላችሁምተቀጥቅጣችሁምተገፍታችሁምየገፋችሁን የቀጠቀጣችሁን ዋጥ አድርጋችሁ የተገላቢጦሽ ይቅርታ መጠዬቅ አለባችሁምወይንም አትነካኩትይመስላል። ስርጉተ በፍጹም– ይህን ትርጉም ይሰጣል የምትይውን ቃል ወይንም አረፍተ ነገር ብታሰይኝ ጽሁፌ ሀሳቤን በትትክክል አልገለጸም ብዬ ለመማር ያስችለኝ ነበር፡፡ ከዚህ የሚያልፍ ከሆነም ይቅርታ ለመጠየቅ ፡፡ ወያኔ የትግሬ ነጻ አውጪ መባሉ ይበዛበታል ግብሩን አይገልጽም ለሥልጣን ሲል ሕዝብ ቢያልቅ ሀገር ቢፈራርስ ደንታ የሌለው ወያኔ እንደምን ነጻ አውጪ ይባላል ወዘተ ማለት እንዴት ሆኖ የዚህ አይነት ትርጉም ሊሰጠው እንደቻለ አይገባኝም ፡፡ በትንሹ የሀውዜንን እልቂት ፤የበደኖን የወተርንና የአርባ ጉጉን ጭፍጨፋ፤የወለጋውን አረመኔያዊ ግድያ ወዘተ ማስታወስ በቂ ይመስለኛል፡፡ እንኳን ይቅርታ ልንጠይቃቸው እነርሱ ልብ ገዝተው አገዛዛችንን ማሰመር አልቻልንም ባይሆን እንኳን አወራረዳችንን እናሳምር ብለው በደላቸውን  በንስሀ ለማስተስረይ ጥፋታቸውን በይቅርታ ለማወራረድ ቢፈቅዱ እንኳን በህግ ተጠያቂ ከሚሆኑባቸው ወንጀሎችና ጥፋቶች ነጻ ሊሆኑ አንደማይችሉ ነው የማምነው፡፡

5- ኢትዮጵዊነታችን ይበልጥብናል፤ ከብዙሃን  ጋር መኖር ይሻለናል ማለትአለባቸው

ትክክል፤-  ይህን ማድረግ የትግራይ ወገኖቻችንን ድርሻና ኃላፊነት ነው ስንል እኛ ደግሞ ወያኔዎች መጠቀሚያ ለማድረግ ሲሉ የሚነዙት አሉባልታና የሚረጩት መርዝ ሀሰት መሆኑን በተግባር ማሳየት ካልቻልን የምንለው ይሆን ዘንድ እንደምን ይቻላል፡፡ ለዚህ ነው ወያኔና ትግረኛ ተናጋሪውን ኢትዮጵያዊ መለየት አለብን፤ በወያኔ ሥልጣን ላይ መኖር ተጠቃሚ ቢሆኑ እንኳን በወያኔ ከሥልጣን መውረድ ተጎጂ እንደማይሆኑ  አምነን ማሳመን ስንችል ነው  ከብዙኑ ጋር መኖር ይሻለናል  ከማለት አልፈው  አታለያየን በስማችን አትነግድብን ወያኔ ዘወር በልልን ማለት የሚችሉት፡፡

6-እኔ የልጆችን መጸሐፍት ስጽፍ እንዴት ተጨንቄ እንደፃፍኩት፤ ምን ያህል ጊዜም እንደበላብኝምአውቃለሁ። እኛ ባለፍነበት ንትርክ እነሱ ማለፍ ስለሌለባቸው ነበር ያን ያህል በጥበብ ድክም ብዬየሠራሁት። የልጆች ራዲዮ ዝግጅቴም እንዲሁ ፍቅርንለማውረስ ይተጋል።  ይህን ሳነብማ እኔና ስርጉተ የባቢሎን ዘመን ሰዎች የሆንን ያህል ተሰማኝ፡፡ አንድ ሀሳብ እያራመድን አንድ ቋንቋ እየተናገርን መግባባት የተሳነን፡፡ እኛ ባለፍንበት ንትርክ ማለፍ የለባቸውም፣  ጥላቻን ሳይሆን ፍቅርን፣  መለያየትን ሳይሆን ተነጋግሮ መግባባትን፣ በአንድ ሀገር ልጅነት ስሜት በፍቅር ተሳስቦ  መኖርን ማውረስ አለብን የምንለው ዘር ሳንመነዝር፣ የቋንቋ ገደብ ሳናበጅ፣ የሀይማኖት ልዩነት ሳንፈጥር ለሁሉም ኢትዮጵያዊ ከሆነ  ወያኔን ነጻ አውጪ ማለት አይገባም በሚል የቀረበው ጽሁፌ ከዚህ አስተሳሰብ አይቃረንም፡፡አልተግባብቶ ሆኖ አንጂ፡፡

በመጨረሻም ወያኔን ከኢትዮጵያ ሕዝብ ጫንቃ ላይ ለማንሳት የሚደረገው የትኛውም ትግል ልንደርስበት የምንፈልገውን ግባችንን አሸጋግሮ በማየት ላይ የተመሰረተ በስሜት ሳይሆን በእውቀት የሚካሄድ በጥላቻ ሳይሆን በአላማ የሚመራ ሁሉንም ኢትዮጵያዊ በእኩልነትና በፍቅር የሚያይ ሊሆን ይገባል፡፡

ወያኔ የሰው ልጅ ይሰራቸዋል ተብሎ የማይታሰብ ድርጊቶችን ፈጽሟል ፤ አሁንም ወደ ፊትም እድሜ እስከሰጠነው ድረስ ሥልጣኔን የሳጣኛል ብሎ የሚፈራውን ነገር ባየ በሰማ  ቁጥር ተመሳሳይ ድርጊት ከመፈጸም ወደ ኋላ አይልም፡፡ የሰራውን ስናስታውስ አረመኔነቱ ሲታሰበን ያደረሰብን ቁስል ሲቆጠቁጠን ጥላቻችን መበረርታቱ ስሜታችን ለበቀል መነሳሳቱ ተፈጥሮአዊ ነው፡፡ እናም ለርኩስ ድርጊቱ የሚመጥን ተመሳሳይ ተግባር መፈጸም እንደሚገባን ሊሰማን ይችላል፡፡ ነገር ግን ክእነርሱ መሻላችንን የምናረጋግጠው፣ ለሀገርና ለሕዝብ የሚበጅ ራዕይ ያለን መሆናችንን የምናሳየው፣ዴሞክራሲያዊት ኢትዮጵያን ለመሻታችን መገለጫ የሚሆነው  ይህን ስሜታችንን ገትተን የዛሬውን ድል ብቻ ሳይሆን የነገውን ውጤት አርቀን እያሰብን ለአላማችን ስኬት ስንታገል ነው፡፡ ደራሲ አያልነህ ሙላት በትያትር እንደገለጸው ኢትዮጵያ በጋሜ እንዳትቀር፡፡

በሰላማዊውም ሆነ በጠመንጃው ትግል በተቻለ መጠን የትግሉን ተሳታፊ ካልሆነም ደጋፊ ማብዛት፤ ብሎም የሚቃወምንና የሚጠላን መቀነስ ፤ በአንጻሩም የተቃራኒን(;ጠላትን)  ጎራ የሰው ኃይል ማሳሳት  ዋንኛ ስትራቲጂ ነው፡፡ ወያኔ ዘረኛ መርዙን የሚረጨው ከፋፋይ ፕሮፓጋንዳውን የሚነዛው በትግራይ ክልል የተሰሩ ግንባታዎችን ወዘተ ጠዋት ማታ የሚነግረንና የሚያሳየን ትግረኛ ተናጋሪውን ወገን ጋሻውና ዋሻው ለማድረግ የያዘውን እኩይ ሴራ ለማሳካት ነው፡፡  ይህን ሴራ ማክሸፍና የረጨው መርዝ ጥፋት እንዳያደርስ ማድረግ የሚገባን እኛ ከወያኔ በተቃራኒ የተሰለፍነው ነን፡፡  ተግባራዊ የሚሆነው ደግሞ ጥላቻን በማሳየት ሳይሆን ፍቅር በመስጠት፣ ጠላቴ ብሎ በማራቅ ሳይሆን ወገኔ ብሎ በማቅረብ፤ የዛሬ ተጠቃሚ ሆነሀል ብሎ በመግፋት ሳይሆን ና ስለነገ አብረን ራዕይ ይኑረን በማለት ወዘተ ነው፡፡ስርጉተ የመንፈስ አብዮት የሚጠይቅ ተግባር ያልሽው መገለጫው ይህ ይመስለኛል፡፡

comment pic

 

Health: የውሃ ምስጢሮች

$
0
0

‹‹እኔ እኮ አይጠማኝም››፤ ‹‹አያስመለክተኝም››፤ እንዲያም ሲል ‹‹ሰው እንዴት ባዶ ውሃ ይጠጣል?›› የሚሉ ሰዎች አጋጥመዋችሁ ይሆናል፡፡ እውነታው ወዲህ ነው፡፡ ፈሳሽ እየወሰዱ ያለ ምግብ ለሳምንታት መቆየት ይቻላል፡፡ የውሃ እጥረት ግን ከማናቸውም ንጥረ ምግቦች እጥረት በተለየ መልኩ በፍጥነት ህይወትን ያሳጣል፡፡ ያለ ውሃ ለ10 ቀናትም እንኳ በህይወት መቆየት አይቻልም፡፡ የሰውነታችን እያንዳንዱ እንቅስቃሴ የውሃን ተሳትፎ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ የሚጠይቅ ነው፡፡ ይሁንና ስለ ውሃ አስፈላጊነት ብዙው ሰው በውል አልተገነዘበውም፡፡ እንዲያውም የንጥረ ምግብ ምድብነቱንም የሚጠራጠሩ ሰዎች አሉ፡፡ ውሃ የሚጠጡት ሊጠማቸው አለበለዚያ ምግብ ሲያንቃቸው ብቻ ነው፡፡
water for health
ከወንዶች የሰውነት ክብደት 60 በመቶ ከሴቶች ደግሞ 50 በመቶ ያህል ውሃ መሆኑ ይታወቃል፡፡ የሰውነት ውሃ መጠን ከወንዶች ይልቅ በሴቶች ላይ አንሶ መገኘቱ ስለ ስብ ክምችታቸው ነው፡፡ ውሃ እና ስብ አያጣጣሙም፡፡ በሰውነታችን ውስጥ ከ38-45 ሊትር የሚገመት ውሃ ይገኛል፡፡ አንጎል 78፣ ደም 83፣ ጡንቻ 75፣ አጥንት 22 በመቶ ውሃ ናቸው፡፡ ዕድሜ እየገፋ ሲሄድ የሰውነት የውሃ መጠን እየቀነሰ፣ የሰውነት ስብ ክምችት እየጨመረ ይሄዳል፡፡ ፆታ፣ ዕድሜ፣ ውፍረት የመሳሰሉት ጉዳዮች የሰውነት ውሃ መጠንን እንደሚወስኑ ልብ ይሏል፡፡

ሰማንያ በመቶ የሚሆነውን ፈሳሽ ፍላጎታችንን የምናሟላው ከምንጠጣው፣ ቀሪውን ሃያ ከመቶ የምናሟላው ደግሞ ከምንበላው ነው፡፡ አትክልትና ፍራፍሬዎች በርካታ ውሃን አዝለዋል፡፡ እንካችሁ ውሃ ከነሙሉ ትጥቁ ይሉናል፡፡ ለምሳሌ ሀብሃብ፣ ቲማቲም፣ ቆስጣ እና ሰላጣ 90 በመቶ ይዘታቸው ውሃ ሲሆን በአቅራቢያችን የሚገኘው ዋጋውም እየተወደደ ያስቸገረን የቫይታሚን ሲ አለኝታችን ‹‹ብርቱካን›› ደግሞ 87 በመቶ ውሃ ነው፤ በፕሮቲን ምንጭነታቸው የምናውቃቸው ሥጋ፣ ዓሣ፣ ዶሮ ሳይቀሩ ከግማሽ እስከ ሁለት ሦስተኛ ይዞታቸው ውሃ ነው፡፡

የውሃ ጠቀሜታ በሰውነታችን ውስጥ ለመጠጥ ፍጆታችን ውሃን እንምርጥ ዘንድ ያሉት ሳይንሳዊ መረጃዎች ግድ ይሉናል፡፡ ከዚህም ሌላ በርካሽ ዋጋ በየቦታው የምናገኘው ጥም ቆራች መጠጥም ውሃ ነው፡፡

ውሃ ማጓጓዣ ነው
ንጥረ ምግቦች እና ወሳኝ ማዕድናት በመላው የሰውነት ክፍሎች የሚዘዋወሩት፤ ቆሻሻ ተረፈ ምርቶች ከሰውነት የሚወገዱት በውሃ ተሸካሚነት ነው፡፡ ያለ ውሃ የሰውነት ዋና ዋና የስራ ሂደቶች ክፉኛ ይስተጓጎላሉ፡፡

ውሃ ማለስለሻ፣ ማለዘቢያም ነው
በውስጣዊ የሰውነት አካላት ዙሪያ የውሃ መኖር እንደ መከላከያ ግድግዳ በመሆን ከውጫዊ ድንገተኛ ጫና ይጠብቃቸዋል፡፡ የዚህ ጥበቃ ተጠቃሚ ከሆኑ የሰውነታችን ብልቶች ውስጥ አንጎል፣ አይን፣ እና ህብለ ሰረሰር ይገኙበታል፡፡
ውሃ በምራቅ እና በሌሎች የሰውነታችን ፈሳሾች ውስጥ በብዛት ስለሚገኝ የተፈጨ ምግብ በጉሮሮ ወርዶ ወደ አንጀት እንዲደርስ የምግብ ቧንቧን የማለስለስ ሚና ይጫወታል፡፡ በተለያዩ ምክንያቶች ምራቅ የቀነሰባቸው ሰዎች ምግብ ለመዋጥ የሚቸገሩት በዚህ ምክንያት ነው፡፡ በተለያዩ የሰውነት ክፍሎች ያሉ የአጥንት መገጣጠሚያዎች እንደልብ እንዲተጣጠፉ አሁንም ውሃ የራሱ ድርሻ አለው፡፡

ውሃ በሰውነት ውስጥ በሚካሄዱ ኬሚካላዊ ዑደቶች ንቁ ተሳታፊ ነው
የፕሮቲን እና የካርቦሃይድሬት ዑደት ልመት ውጤቶች የሰውነት ህዋሳት በሚጠቀሙበት መልኩ እንዲቀየሩ ውሃ የሚጫወተው ሚና በቀላሉ የሚታይ አይደለም፡፡ እንደ ተረፈ ምርት ሆኖ ከሰው ሰራሽ ብክለት ነጻ የሆነ አንድ ብርጭቆ ያህል ውሃ በየቀኑ በዚህ መልኩ ይፈጠራል፡፡ እኛ እንገነዘበው ይሀናል እንጂ ህዋሳት ለዕለት ፍጆታቸው ፈጥኖ የሚያደርስላቸው በመሆኑ ውሃን በጉጉት ይጠብቁታል፡፡

ውሃ የሰውነት ሙቀትን ይቆጣጠራል
በጤና እንሰንብት ዘንድ የሰውነታችን ሙቀት ተገቢ በሆነ ልክ ተወስኖ መቆየት አለበት፡፡ የውጪው አየር ሙቀት ሲለዋወጥ የሰውነታችን ሙቀት አብሮ አይለዋወጥም፡፡ ይህም የሆነበት ዋናው ምክንያት ሰውነታችን አብዛኛውን እጅ ውሃ በመሆኑ፣ ውሃ ደግሞ በተፈጥሮው የሙቀት ለውጥ የሚያስተናግደው ዝግ ብሎና ተረጋግቶ ስለሆነ ሙቀትን አፍኖ ይይዛል፡፡
በሞቃታማ የአየር ንብረት ወቅት ከሰውነታችን ውስጥ የውሃ ትነት ይከሰትና አላስፈላጊ ሙቀት አብሮ እንዲወገድ ያደርጋል፡፡ በዚህም ላይ ላብ አለ፡፡ ሳናስተውለውም ቢሆን ቀንና ሌሊት ያልበናል፤ በተለይ በሞቃት የአየር ንብረት እና በከፍተኛ አካላዊ እንቅስቃሴ ወቅት የላብ መጠን ይጨምራል፡፡
ከዚህም በተጨማሪ ውሃ ቆዳችንን በማለስለስ ውበትን እንደሚያጎናፅፍ ይታወቃል፡፡ የስነ ቆዳ ውበት ባለሙያዎች መፍቀሬ ውበት ወይዛዝርት ደንበኞቻቸውን አበክረው የሚመክሩት ዘወትር ውሃ በበቂ ሁኔታ እንዲጠጡ ነው፡፡

የሰውነት ፈሳሽ ሚዛን መጠበቅ
ሰውነታችን በየቀኑ የውሃ ብክነት ከውሃ አወሳሰድ ጋር እንዲመጣጠን የሚያስችል ውስጣዊ አሰራር አለው፡፡ የፈሳሽ እጥረት ሲያጋጥም ኩላሊቶች መልኩ ቡናማ የሆነ መጠኑ ያነሰ ፈሳሽ በሽንት መልክ እንዲወገድ በማድረግ የሰውነት ፈሳሽን ይቆጥባሉ፡፡ በተጨማሪም አንጎላችን ዝም አይልም፤ የውሃ ጥምን በማወጅ ፈጥነን ውሃ እንድንጠጣ ያሳስባል፡፡ የፈሳሽ ሚዛኑ ወደ መበራከት ካመዘነ ኩላሊቶች የጠራ ሽንትን አብዝተው ያመርታሉ፡፡ አንጎል በበኩሉ ውሃ ጥምን ያነሳል፡፡

ውሃ ከሰውነታችን የሚወገድባቸው መንገዶች
በሚታይና በማይታይ መልኩ ውሃ ከሰውነታችን ይወጣል፡፡ ቆዳ፣ ኩላሊቶችና ሳንባዎች በውሃ መወገድ ሂደት ዋና ዋና ተሳታፊዎች ናቸው ማለት ይቻላል፡፡ ዝርዝሩን ቀጥለን እንመልከት፡፡

በቆዳ በኩል
የሰውነት ሙቀትን ለመቆጣጠር ከሚያስችሉ ዘዴዎች አንዱና ዋነኛው በቆዳ በኩል ውሃን ማውጣት ነው፡፡ ይህም እንደ አካባቢው የሙቀት መጠን እና እንደ አካላዊ እንቅስቃሴ ሁኔታ ይለያያል፡፡ በአማካይ በላብ በኩል የሚወገደው የውሃ መጠን 100 ሚሊ ሊትር ነው፡፡
በሞቃት አካባቢዎች የሚኖሩ ሰዎች ውስጣዊ የሰውነታቸውን ሙቀት ለመቆጣጠር ሲባል በቀን እስከ 2 እና 3 ሊትር የሚደርስ ላብ ሊያልባቸው ይችላል፡፡ ይህን የሚተካ ውሃ ካልተወሰደ የፈሳሽ ሚዛኑ እንደሚዛባ መገመት አያዳግትም፡፡ አድካሚ የሆነ አካላዊ እንቅስቃሴ ከታከለበት ደግሞ ሁኔታውን ይበልጥ ያባብሰዋል፡፡
የሰውነት እንቅስቃሴ ከወትሮው በጨመረ ቁጥር የሰውነት ሙቀትም ይጨምራል፡፡ ታዲያ ተማሪው ሙቀት መወገድ የሚችለው በላብ አማካኝነት ነው፡፡ ከፍተኛ ደረጃ ስፖርታዊ እንቅስቃሴዎች የላብን መጠን 1 ሊትር በሰዓት ሲያደርሱት ይህ ድርጊት በሞቃታማ አካባቢ ከሆነ ግን በላብ የሚወገደው የውሃ መጠን 2 እና 3 ሊትር በሰዓት ሊደርስ ይችላል፡፡
በበሽታ ምክንያት የሚመጣ የሰውነት ትኩሳት ሌላው ላብ አምጪ ጉዳይ ነው፡፡ የሰውነት ሙቀት ከተለመደው በ1 ዲግሪ ሴልሽየስ ከጨመረ የላብ መጠን በግማሽ ሊትር ይጨምራል፡፡ ትኩሳት ላለባቸው ሰዎች ተጨማሪ ፈሳሽ እንዲወስዱ ሐኪሞች የሚመክሩት ለዚህ ነው፡፡
ላብ የሚታይ ነገር ነው፡፡ የማይታ ነገር ግን በቆዳ በኩል የሚባክን ውሃ አለ፡፡ ስለ እርሱ ጥቂት ላውጋችሁ፡፡ ውሃ ከቆዳችን ያለማቋረጥ በትነት መልኩ የሚወጣ ሲሆን መጠኑም በቀን 350 ሚሊ እንደሚደርስ ይገመታል፡፡ የቆዳ ላይ ትነት እና ላብ አይገናኙም፡፡ አንድ አስገራሚ ማስረጃ ላቅርብ፡፡ ያለ ላብ አመንጪ ዕጢዎች የሚፈጠሩ ሰዎች አሉ፡፡ (እንዲህ ያለ ሰው ገጥሞኛል) ታዲያ ሰዎቹ በምንም አይነት ሁኔታ ውስጥ ሆነው ባያልባቸውም ሊከሰት ይችል የነበረውን ከፍተኛ የሰውነት ሙቀት መጠን በቆዳ ትነት አማካኝነት ይከላከሉታል፡፡ ይህ ባይሆን ኖሮ ምን ይውጣቸው ነበር?

በኩላሊቶች በኩል
ከሰውነት በኩላሊቶች አጣሪነት የሚወገደው የሽንት መጠን በሆርሞን ቁጥጥር ስር ያለ እና የሰውነት የፈሳሽ ሚዛንን ለመጠበቅ ሲባል ወቅታዊ ማስተካከያ የሚደረግበት ነው፡፡ ብዙ ፈሳሽ እየወሰደ የሚገኝ ግለሰብ ብዛት ያለው ጠራ ያለ ሽንት ሲኖረው በአንፃሩ የፈሳሽ አወሳሰዱ የቀነሰ ሰው የሚኖረው ሽንት መልኩ የደፈረሰ፣ መጠኑ ያነሰ ነው፡፡ ይህ ቀላል የሽንት ቀለምን የመለየት ዘዴ የሰውነት የፈሳሽ ሚዛንን ለመገምገምና የእርምት እርምጃ ለመውሰድ ያስችላል፡፡ የሰውነት ፈሳሽ እጥረት ሲያጋጥም ኩላሊቶች ውሃን በመቆጠብ ስራ ይጠመዱና በሽንት መልክ እንዲወገድ የሚፈቅዱት የፈሳሽ መጠን ከግማሽ ሊትር አይበልጥም፡፡ በተቃራኒው ሰውነት በውሃ ብዛት ሲንበሸበሽ በቀን እስከ 20 ሊትር ውሃ በሽንት መልክ ማስወገድ እንደሚችሉ ያስመሰክራሉ፡፡ በአዘቦቱ ቀን የሽንት መጠን ከ1.3 እስከ 1.4 ሊትር ነው፡፡ ፕሮቲንና ጨው የበዛባቸው ምግቦች እንዲሁም የአልኮል መጠጦች ሽንትን በማብዛት ይታወቃሉ፡፡

በሳንባዎች በኩል
በአፍ እና በአፍንጫ ተስቦ የሚገባው አየር ከመተንፈሻ አካላት ስስ ልባስ በሚለገሰው እርጥበት ምክንያት ለውስጥ ሰውነት ወደ ሚስማማ እርጥበታማ አየር ይቀየራል፡፡ ውሃ ለእርጥበት መፈጠር ዋናው ግብዓት መሆኑን መገንዘብ ያስፈልጋል፡፡ ያለማቋረጥ በትንፋሽ የሚጠፋው የውሃ መጠን ከ350-400 ሚሊ በቀን ይገመታል፡፡
በትንፋሽ በኩል የሚወጣው የውሃ መጠን ያካባቢው አየር እርጥበት ሲቀንስ፣ ኤር ኮንዲሽነር ባለበት ክፍል፣ በተራራማ ቦታዎች፣ አይሮፕላን ውሰጥ እና በስፖርታዊ ልምምድ ወቅት ይጨምራል፡፡ እንደ አሁኑ ባለ ቀዝቃዛ ወራት በትንፋሽ የሚጠፋው ውሃ ይበራከታል፡፡ ለዚህም ነው በቅዝቃዜ ወቅት የአፍና አፍንጫ ውስጥ ድርቀትን የሚያስተናግዱት፡፡

በዓይነ ምድር በኩል
በቀን ከመቶ ሚሊ ሊትር ያልበለጠ ውሃ ከአይነ ምድር ጋር አብሮ ይወገዳል፡፡ ሰዎች እንደ ኮሌራ በመሰሉ አጣዳፊ የተቅማጥ በሽታዎች ሲያዙ ይህ አሃዝ በማይታመን መልኩ ወደ 1 ሊትር በሰዓት ሊያሻቅብ ሲችል አፋጣኝ የፈሳሽ መተካት ህክምና ካልተደረገ በአጭር ጊዜ ውስጥ ህይወትን ሊያሳጣ የሚችል ነው፡፡

ለውሃ እጥረት የተጋለጡ
ህፃናት

የማላብ ስርዓታችን ገና ስላልዳበረ ከፍ ያለ ሙቀት መቋቋም ይሳናቸዋል፡፡ ይህም ብቻ አይደለም፣ ለውሃ ጥም ስሜት እንደ አዋቂዎች ያለ አፀፋዊ ምላሽ አይሰጡም፡፡ አጣዳፊ ትውከትና ተቀማጥ ካጋጠማቸው ደግሞ ለሰውነት መሟሸሽ ፈጥነው ይጋለጣሉ፡፡
አረጋውያን

እንደ ወጣቶቹ ሰውነታቸው ውሃ ሲያጥረው ስለማይጠማቸው ለሰውነት መሟሸሽ ተጋላጭ ናቸው፡፡ ተደራራቢ በሽታዎች ለእነዚህም የሚወሰዱ መድሃኒቶች ካሉ የውሃ እጥረት ችግሩ ይባባሳል፡፡
ህፃናትና አረጋውያን በቂ ውሃ እንዲያገኙ ማስቻል ከቤተሰብ አባላት እንዲሁም ከህብረተሰቡ የሚጠበቅ በጎ ተግባር ነው፡፡

አትሌቶች

ከሌሎቹ ንጥረ ምግቦች ይልቅ የውሃ አወሳሰዳቸው ትኩረትን የሚሻ ጉዳይ ሆኖ እናገኘዋለን፡፡ ውሃ ፈርጣማ ጡንቻዎቻቸውን ለማብረድ፣ የሰውነታቸውን ሙቀት ለመቆጣጠር ቁልፍ ሚና ይጫወታል፡፡ የውሃ እጥረት ስፖርታዊ ክንውናቸውን ክፉኛ የማወክ ዝንባሌ ሲኖረው መዘዞችም አሉት፡፡ ለምሳሌ አንድ አትሌት ከሰውነት ክብደቱ ከ2-3 በመቶ ያለው በላብ ምክንያት ቢቀንስ በአግባቡ ተልዕኮውን ማከናወን ይሳነዋል፡፡ የፈሳሽ ጉድለቱ ከ7-10 በመቶ ከደረሰ ግን ሰውነት ከአቅም በላይ በሀነ ግለት ይመታና ከዚህች ዓለም ስንብት ይሆናል፡፡ የማራቶን ሯጮች በአንድ ሰዓት ውስጥ እስከ 2.8 ሊትር የሚገመት ላብ ያልባቸዋል፡፡ በስፖርታዊ ልምምድም ሆነ በውድድር ወቅት ከሚከሰት ከፍተኛ የፈሳሽ እጥረት ለመከላል ከድርጊቱ አስቀድሞ (2 ብርጭቆ ውሃ ከ2 ሰዓት በፊት፣ 1 ብርጭቆ ውሃ ከ15 ደቂቃ በፊት)፣ በክንዋኔው ወቅት (በየ20 ደቂቃው ከግማሽ እስከ 1 ሙሉ ብርጭቆ) እና ከውድድሩም በኋላ በቂ ውሃ መጠጣት ያስፈልጋል፡፡
ከዚህም ሌላ ከቤት ውጭ ባልተከለለ ቦታ ቀኑን ሙሉ የሚሰሩ ሰዎች ለፈሳሽ እጥረት የተጋለጡ ናቸው፡፡ ሞቃትና ከፍተኛ የአየር እርጥበት ከልፋት ጋር ሲደመሩ የፈሳሽ እጥረቱን ያባብሱታል፡፡ እንዲህ ያሉ ሠራተኞች ከጎናቸው ውሃ ሳይለያቸው በመካከል ውሃ ቢጎነጩ መልካም ነው፡፡

ለምን ይጠማናል?
ሰውነታችን የውሃ ፈሳሽ እጥረት እንዳጋጠመው አብዛኛውን ጊዜ የሚያስታውቀው ጥምንን በማወጅ ነው፡፡ አንድ ሰው የጥም ስሜትም ሆነ የህመም ስሜት ሳይሰማው የሽንቱ መጠን ሳይቀንስ መልኩም ሳይደርስ የጠራ ከሆነ ግለሰቡ የፈሳሽ ሚዛኑ የተጠበቀ ነው ብሎ መገመት ይቻላል፡፡ ታዲያ ሁሌም እንዲህ አይሆንም፡፡ ልማድ አድርገነው ውሃ እስኪጠማን ድረስ ሳንጠጣ የምንቆይ ከሆነ አንዳንዴ ሰውነታችን የፈሳሽ እጥረት እንኳ ገጥሞት አንጎላችን ጥምን ሳያውጅ የሚቆይበት ጊዜ አለና በየጊዜው በቂ ውሃ መውሰድ የዕለት ተዕለት ተግባራችን ሊሆን ይገባል፡፡ በተለይ ህፃናት፣ አረጋውያን፣ ስፖርተኞች፣ እና አትሌቶች የሰውነት ውሃ ፍላጎታቸው በጥም ላይ ሊመሰረት አይገባውም፡፡

በየቀኑ ምን ያህል ውሃ መጠጣት አለብን?

እያንዳንዱ ሰው በጤና ለመሰንበት በቂ ውሃ በየቀኑ መጠጣት ይኖርበታል፡፡ ይህ መጠን እንደሰውየው ዕድሜ፣ ፆታ፣ ጤና እና አካላዊ እንቅስቃሴ ሁኔታ ይለያያል፡፡ የአየር ሁኔታውም ተፅዕኖ አለው፡፡ በደምሳሳው ሲታይ ከባድ የሰውነት እንቅስቃሴ የማያደርግ፣ በምቹ የአየር ንብረት ያለ አንድ ጤናማ አዋቂ ሰው በቀን አነሰ ከተባለ 2 ሊትር (8 ብርጭቆ) አለበለዚያ 3.5 ሊትር (13 ብርጭቆ) ውሃ መጠጣት ሲያስፈልገው ካላቸው የስብ ክምችት የተነሳ የሴቶች የውሃ ፍላጎት ከወንዶቹ በአማካይ በ1 ሊትር ያንሳል፡፡
ውድ አንባብያን በቂ ውሃ የመጠጣት ልምድን ለማዳበር ከዛሬ ጀምሩ፤ በቀስ በቀስ የውሃ አወሳሰድን አጎልብቱ! ለዚህ እኔ ምስክር ነኝ፣ ከ2 ብርጭቆ ተነስቼ አሁን ላይ 13 ብርጭቆ ደርሻለሁ፤ ቤተሰቦቼም እንደኔ የመጠጥ ውሃ ይደፍራሉ፡፡

አብዛኛው የህብረተሰብ ክፍል ከመደበኛው በታች የሆነ የፈሳሽ አወሳሰድ ስላለው በመለስተኛ የሰውነት መሟሸሽ ደረጃ ውስጥ እንደሚገኝ ይገመታል፡፡ ስር የሰደደ የሰውነት ፈሳሽ እጥረት ለኩላሊት ጠጠር እና ሌሎች መዘዞቹ እንደሚዳርግ የሞያ ተሞክሮዬ አስገንዝቦኛል፡፡ የህክምና መጻህፍት ከዚህ ጋር ይስማማሉ፡፡
በእነዚህና እነዚህ ምክንያቶች የተነሳ ውሃ ለህይወታችን መሰረት ነው፤ ውሃ ህይወት ነው እላለሁ!
ቸር እንሰንብት፡፡

አሻራ መጽሄት – ቁጥር 2 (ፕ/ር መስፍን ወልደማርያም፣ ጸጋዬ ገብረመድህን አርአያ፣ ዩሱፍ ያሲን፣ ደረጀ ደስታ…)

$
0
0

Mesfin– ጸጋዬ ገመዴህን አርአያ – “ጠፍአት አገርነ” ትናንት ማታ ጨረቃዋንም አዋልደናል! – ዩሱፍ ያሲን – የአረቡ ዓለም መቆራቆስ ቀይ ባህርን ይሸጋገር ይሆን? – ደረጀ ደስታ – ቆም በል! ህዝብ ከሚያልቅ ህዝብ ቢያልቅ ይሻላል! – ቆይታ ከፕሮፌሰር መስፍን ወልደማርያም ጋር እና ሌሎችም[ሙሉውን ለማንበብ እዚህ ይጫኑ]—–

 


አርበኞች ግንቦት 7 በሁመራ በተደረገ ውጊያ ከሕወሓት መንግስት 40 ወታደሮችን ገደልኩ; ከራሴ 10 ተሰዉብኝ አለ

$
0
0

Arbegoch Ginbot 7
(ዘ-ሐበሻ) አርበኞች ግንቦት 7 በበተነው መረጃ መሠረት ዛሬ በሰሜን ጎንደር ሁመራ አካባቢ በተደረገ ውጊያ ከ40 በላይ የስርዓቱን ቅጥረኞች ገደልኩ አለ:: ግንባሩ በበተነው መረጃ ከራሱ ወደ 10 የሚጠጉ ሰራዊቶች መሰዋታቸውን ገለጸ::

ዛሬ በሕወሓት አስተዳደር በኩል ምንም የተባለ ነገር ባይኖርም አርበኞች ግንቦት 7 ባወጣው መግለጫ ግን በርካታ የስርዓቱ ወታደሮች አገዛዙን እየከዱ ግንባሩን ከመቀላቀላቸውም በርካቶች ጠመንጃቸውን እየጣሉ ንቅናቄውን እየተቀላቀሉ መሆኑን አስታውቋል::

አርበኞች ግንቦት 7 በሰሜን በኩል የጀመርኩትን ውጊያ የማቆመው ድል እስከማደርግ ድረስ ነው ሲል ዘግቧል::

ከደርግ የባሰ ግፍ በጎንደር

$
0
0

– የሚሊዮኖች ድምጽ

ወያኔ/ኢሕአዴግ “ብሶት ነው የወለደኝ” በሚል ደርግን በሚዋጋበት ጊዜ፣ መንገድ አሳልፎ ወደ መሃል አገር እንዲገባ ያደረገው የጎንደር ሕዝብ ነበር። በመላኩ ተፈራና በደርግ መከራን ያየና በመከራ የተማረረ ህዝብ፣ የተሻለ ሊመጣ ይችላል በሚል ነበር ወያኔን አሳልፎ ያስገባው።
ሆኖም ጎንደሬው ከደርግ የባሰ ግፍና መከራ እየደረሰበት ነው። ደርግ ያላደረገው በደል ህዝቡ እየተፈጸመበት ነው። ገበሬው ከምርታማ የጎንደር መሬት በኃይል እየተፈናቀለ ፣ ለአገዛዙ ቅርበት ላላቸው ኢንቨርስትሮች መሬቱ እየሰጠበት ነው። እሰ ሰሊጥ የመሳሰሉት የሚያበቅለው ለምለሙ መሬት በኢንቨርስተሮች ሕግ ወጥና ጸረ-ሕዝብ በሆነ መንገድ እየተወረረ ነው። ይሄን አይነት ዜጎችን ማፈናቀል ደርግ እንኳን ያልፈጸመው ግፍ ነው።
በምእራብ ወያኔ ገበሬዎችን ቀምቶ የጎንደርን መሬት ለሱዳን አሳልፎ እየሰጠ ነው። ይሄንን በደርግ ጊዜ ያልታየ ለኢትዮጵያ ህዝብ ጥም መቆም ሳይሆን አገርን መሸጥ መሆኑን የሚያሳይ ነው።
Gonder
ሕዝቡ ለመብቱ፣ ለክብሩ፣ ለነጻነቱ ሰላማዊ በሆነ መንገድ ጥያቄ ሲያነሳ ደግሞ እየተደገደል፣ እየታሰረ፣ ክፍተኛ እንግክትና መከራ እየደረሰበት ነው። በኢትዮጵያ በሰለጠነ መልኩ በሰላም ለዉጥ እንዲመጣ ሲንቀሳቀሱ የነበሩ ታጋዮች ብዙዎቹ ሲሰደዱ፣ ብዙዎቹ ወህኒ ወርደዋል። በአንድነት ፓርቲ ሥር በጎንደር ክፍል ሃግር ሲንቀሳቀሱ ከነበሩ ጀግና ወገኖቻችን መካከል የሚከተሉት ይገኙበታል።
1. ኣንጋው ተገኝ (ሰሜን ጎንደር)
2. አባይ ዘዉዱ (አብርሃ ጅራ ጎንደር)
3. እንግዳው ዋኘው (አብርሃ ጅራ ጎንደር)
4. በላይነህ ሲሳይ (መተማ ጎንደር
5. አለባቸው ማሞ (መተማ ጎንደር)
6. አለበል ዘለቃ ሃይማኖት አየና ( ውሮታው፣ ደቡብ ጎንደር)
7. ጸጋዬ ገበይየሁ (አርማጭሆ)
8. መምህርት ግዛው ( ሰሜን ጎንደር)
9. አውቀ ብርሃኑ (ጎንደር)
10. ማሩ አሻግሬ ( የአርማጭሆ ተወላጅ፣ የዞኑ የአንድነት አመራር – ቀይ የለበሰው))
11. አለላቸው አታለለኝ ( የሰሜን ጎንደር አንድነት ሰብሳቢ)
12. አስቴር ስዩም ( በጎንደር የምእራብ አርማጮሆ የአንድነት አመራር)

በሕወሓት $5 ሺህ ዶላር የተደለለው ድምፃዊ ደረጀ ደገፋው በዲሲ ከፍተኛ መገለል እየደረሰበት ነው

$
0
0

Dereje Degefaw
ቢሆነኝ ከዋሽንግተን ዲሲ

የሕወሓት መንግስት በሰሜን አሜሪካ ያሉ ኢትዮጵያውያንን ለመከፋፈል የኢትዮጵያ ስፖርት ፌዴሬሽን በሰሜን አሜሪካ ላይ አንጃ በመፍጠር በስርዓቱ ደጋፊ በሼህ መሀመድ አላሙዲ ሌላ ፌዴሬሽን አቋቁመው በኢትዮጵያውያን ቦይኮት መደረጋቸው ይታወሳል:: ከአንድ ዓመት በፊት የወያኔ መንግስት በሚኒሶታ ባዘጋጀው የስፖርት ፌስቲቫል ላይ ትናንት ሃገር ወዳድ በመምሰል ስለታማኝ በየነ ጀግንነት እያወደሰ ሲዘፍን የነበረው ድምፃዊ ደረጀ ደገፋው ከአላሙዲ የተከፈለው 5 ሺህ ዶላር በልጦበት ሃገር ወዳዱን ኢትዮጵያዊያን ክዶ ተገኝቶ ነበር::

ይህ ድምፃዊ ለገንዘብ ራሱን በማስገዛቱ እጅጉን በ”መጸጸቱ” በዲሲ ባሉ ራድዮኖችና ዲሲን መሠረት ባደረጉ ሚድያዎች እንዳይዘገብበት አርቲስት ታማኝ በየነ እና አበበ በለው እግር ስር መውደቁ ይነገራል:: በወቅቱ የደረጀ ደገፋው ለገንዘብ ሲል ለወያኔ ፌስቲቫል ማድመቂያ መሆኑን እነዚሁ ሚድያዎች ዝም ብለውለት አለፉ:: ሆኖም ግን ሕዝቡ ዝም አላለም:: ይበላበት የነበረበት ሬስቶራንትና የሚውልበት አካባቢ ያሉ ኢትዮጵያውያን ለገንዘብ ሲል ለወያኔ ራሱን የሸጠ እያሉ ማግለል ጀመሩ::

ድምፃዊው ቀጥሎም የአምናው ሳያንስ ዘንድሮም ሕወሓት በአላሙዲ ስፖንሰርነት ዴንቨር ላይ ባደረገውና ቦይኮት በተደረገው ኳስ ጨዋታ ላይ ዘፍኖ ተመልሷል:: ትናንት እነ አቦነሽ አድነውን ቦይኮት አስደርገው ሬስቶራንቷን እንድትዘጋ ያደርጉ የዲሲ ራድዮ ጣቢያዎችና አክቲቭስቶች ደረጀ ደገፋውን ዝም ቢሉትም ሕዝቡ ግን ድምፃዊውን ከማግለል አልተመለሰም:: በዲሲ ብዙ ጊዜ ከሚዝናናበት ካፌ ከሕዝቡ በሚደስበት ተቃውሞ ለመቅረት ተገዷል:: በአሁኑ ወቅት ይህ ድምጻዊ ራሱን ከኢትዮጵያውያን እየደበቀ ለታማኝ ዘፍኖ ያገኘውን ክብር በሕወሓት $5 ሺህ ዶላር ሸጦታል::

ማሳሰቢያ በተለይ ለዲሲ ራድዮኖችና አክቲቭስቶች:- ከወያኔ ጋር ያበረውን ድምፃዊም ሆነ አርቲስት ቦይኮት ማድረጋችሁን እኮራበታለሁ:: ሆኖም ግን ከአንድ አካባቢ ነው የመጣነው በሚል ከወያኔ ጋር ያበረውን አርቲስትም ዝም አትበሉት:: ዘር ቆጠራ ውስጥ ከገባችሁ እናንተም ከወያኔ አትሻሉም::

ጉደኛው አርከበ እቁባይ “ወደብ ልማት ያመጣል ብለው የሚያስቡ ሰዎች ስለ ኢኮኖሚ ልማት ምንም የማይገባቸው ሰዎች ናቸው”አሉ

$
0
0

የጠቅላይ ሚኒስትር ልዩ አማካሪ አቶ አርከበ እቁባይ ግንቦት 20ን አስመልክቶ ከዘመን መጽሔት ጋር ቆይታ አድርገዋል። ከቀረበላቸው ጥያቄ መካከል ድርጅትና መንግሥታቸው ኤርትራንም ሆነ ወደቡንም አሳጥቶናል የሚሉ ወገኖች አሉና ለእነዚህ ወገኖች ምላሽዎ ምንድን ነው? የሚለው አንደኛው ነበር። እንዲህ ብለው መለሱ-
Arkebe Equbay
“ስለ ሕዝብ የማያነሳና የማያስብ ግለሰብ ወይም ቡድን ብቻ ነው ስለ መሬትና ወደብ የሚያነሳው። አገር ማለት ሕዝብ ነው። ስለሆነም ስለ ሕዝቦች በምናስብበት ጊዜ የኤርትራ ሕዝብ እንደ ሕዝብ ነው መወሰድ ያለበት።” በማለት የጀመሩት አርከበ ስለ ኤርትራ ህዝብ ፍላጎትና ስለድርጅታቸው አቋም እንዲህ ብለዋል “ የኤርትራ ሕዝብ ምን ይፈልጋል? ለብዙ ዓመት በጦርነት ውስጥ የቆየ ሕዝብ ነው፤ ከ30 ዓመታት በላይ። ከኢትዮጵያ መገንጠል እንፈልጋለን አሉ። 99 በመቶ የሚሆነው የኤርትራ ሕዝብ ነፃ ኤርትራን እንፈልጋለን አለ። ሕዝቡ ፍላጐቱን በድምፅ አረጋገጠ ማለት ነው። የሕዝቡ ፍላጐት ደግሞ መሟላት አለበት። ዴሞክራሲ ማለት ለሕዝብ መቆም ማለት ነው። ማነው የመጀመሪያ
አገር ኤርትራን እንደ አገር የተቀበለው? የኢትዮጵያ መንግሥት ነበር። ያ ሆኖ ሰላም ማረጋገጥ ተችሏል። ስለዚህ ያንን ያደረግነው ከሰላም፣ ከዴሞክራሲ፣ ከሕዝቦች መብት ማረጋገጥ አንፃር ነውና ይሔ መሆኑ ተገቢ ነው።”

ወደብን አስመልክቶ ግን አቶ አርከበ የሰጡት ማብራሪያ “የአሰብን ወደብ (ባለመጠቀም) የግመል መጠጫ ሆኖ ይቀራል (እናደርገዋለን?) በማለት ዝተው ከነበሩት ከአቶ መለስ ዜናዊ ንግግር ጋር የሚመሳሰል ይመስላል። “እኛ ወደብ መች ቸገረን?” ያሉት አቶ አርከበ ወደብ ብቻውን ልማትን የማያስገኝ መሆኑን በመግለጽ ጥያቄውንም ሆነ ባለወደቢቷን ኤርትራን ከሶማልያ ጋር በመደመር ያናናቁ መስለዋል። እንዲህ ብለዋል-
“ግን ዋናው ነጥብ ምንድንነው ወደብ ልማት ያመጣል ብለው የሚያስቡ ሰዎች ስለ ኢኮኖሚ ልማት ምንም የማይገባቸው ሰዎች ናቸው። በአካባቢያችን ሠፋፊ ወደብና የባህር ዳርቻ ያላቸው አገሮች እነማን ናቸው? አንዷ ሶማሊያ ናት። ሁለተኛዋ ማናት? ኤርትራ
ናት። ሁለቱንም እንያቸው በጥፋት ሂደት ያሉ አገሮች ናቸው። ሶማሊያ ግን አሁን በተሻለ እንቅስቃሴና
መረጋጋት ውስጥ ናት። ኢኮኖሚ ልማት በእነዚህ አገራት የለም። ስለዚህ ልማትና ዕድገትን የሚያመጣው ወደብና የባህር ዳርቻ ነው የሚለው አስተሳሰብ ሕዝብን እንደ ሕዝብ ያለ ማየት አስተሳሰብ ምንጭ ነው። እኛ ወደብ መች ቸገረን? በጂቡቲና በበርበራ መጠቀም እንችላለን። የኤርትራም ሁኔታ መቀየሩ አይቀርም፡፡ አሁን ያለው ሁኔታ ለዘለዓለም ይኖራል ብለን አንገምትም። በእኔ ግምት በሚቀጥሉት አስር ዓመታት ውስጥ ለውጥ ይመጣል ባይ ነኝ። የኤርትራን ወደብ እንጠቀማለን። የኬንያን ወደብ መጠቀም እንችላለን። ከዚያ ወደ ኢትዮጵያ የሚገባ መስመር ለመገንባት ታቅዷል። የሱዳንንም እንጠቀማለን። ቢቻል ወደብ ቢኖረን ጥሩ ነበር ግን የሁሉም መቋጫና መፍትሔ እርሱ ነው ማለት አይደለም። የሚያመጣው መሠረታዊ ለውጥም የለም በእኔ እምነት።”

የሰው መጽሐፍ ታሪክን በፊልም ካለፈቃድ ወስዶ ሰርቷል በሚል በ10 ሚሊዮን ብር የተከሰሰው አርቲስት ቴዎድሮስ ተሾመ ለሐምሌ 23 ተቀጠረ

$
0
0

maxresdefault
በአርቲስት ቴዎድሮስ ተሾመ “ሦሥት መዓዘን” ፊልም እና በደራሲ አትንኩት ሙሉጌታ “ፍቅር ሲበቀል” የተሠኘ ረጅም ልብወለድ መፅሐፍ መካከል የነበረው የ10 ሚሊዮን ብር የፍትሐብሔር ክስ ክርክር ለፍርድ ማስፈፀሚያ የሚሆን ብር ማስያዣ ማቅረብ ይችላል የሚል ሀሣብ አርቲስት ቴዎድሮስ ተሾመ ባቀረበው ተቃውሞ መሠረት ከጥቅምት 22/2007 ዓ.ም ጀምሮ ሲከራከሩ መቆየታቸው ይታወቃል፡፡

በመሆኑም ሰኔ 24/2007 ዓ.ም የልደታ ከፍተኛ ፍርድ ቤት 13ኛ ምድብ በዋለው ችሎት የደራሲ አትንኩት ሙሉጌታ ጠበቃ አቶ አንዱዓለም በእውቀቱ እና የአርቲስት ቴዎድሮስ ተሾመ ጠበቃ አቶ ኤልያስ ተ/መድህን ያቀረቡትን አቤቱታ ዳኛው ግራ ቀኙን ካዩ በኋላ ብይን የሠጡ ሲሆን አርቲስት ቴዎድሮስ ለሐምሌ 23/2007 ዓ.ም ለተከሰበት ክስ መልስ ይዞ እንዲቀርብ ዉሳኔ ሲሰጡ ከዚህም ጋር አያይዘውም የመፅሀፉን አንድ ኮፒ አብረዉ ሠጥተዋል፡፡

ከሳሽ ደራሲ አትንኩት አርቲስት ቴዎድሮስ ተሾመ ለእይታ ያበቃው “ሦስት ማዕዘን” የተሰኘ ፊልም ታሪክ በ2000 ዓ.ም ካሳተሙት “ፍቅር ሲበቀል” የተሰኘ የረዥም ልቦለድ መፅሃፍ የተወሰደ ነው የሚል አቤቱታ ማሰማታቸውን ዘ-ሐበሻ ከዚህ ቀደም መዘገቧ አይዘነጋም::

Health: የአንድ ሰው አካል 100 ትሪሊዮን በሚያህሉ ጥቃቅን ሴሎች የተገነባ ነው –ለመሆኑ ሴል ማነው? ስራውስ?

$
0
0

Boday cells
የአንድ ሰው አካል 100 ትሪሊዮን በሚያህሉ ጥቃቅን ሴሎች የተገነባ ነው፡፡ ጠቂቶቹን ለመጥቀስ ያህል የአጥንት ሴሎች፣ የደም ሴሎችና፣ የአንጎል ሴሎች ይገኙበታል፡፡ በአካላችን ውስጥ ከ200 የሚበልጡ የተለያዩ የሴል አይነቶች ይገኛሉ፡፡

ከላይ የጠቀስናቸው ብዛት ያላቸው የሴል አይነቶች ቅርፃቸውና ስራቸው ቢለያይም እጅግ ውስብስብ በሆነ መንገድ ተቀናጅተው ይሰራሉ፡፡ በዘመናችን ልዩ የሚባሉት እንደ ኮምፒዩተር ያሉ የቴክኖሎጂ ውጤቶች፣ የኢንተርኔት መረጃ መረቦች እንኳ ከእነዚህ ሴሎች ጋር ሲነፃፀር በጣም ቀርፋፋ ነው፡፡

ሴልና ህልውና
ሴሎች ሁሉም ኒውክሊዮስ ያላቸውና የሌላቸው ተብለው በሁለት ይከፈላሉ፡፡ የሰው፣ የእንስሳትና የዕፅዋት ሴሎች ኒውከሊዮስ አላቸው፡፡ የባክቴሪያ ሴሎች ደግሞ ኒውክሊየስ የላቸውም፡፡ ኒውክሊየስ ያላቸው ሴሎች ዩካርዮቲክ ይባላሉ፡፡ ኒውክሊየስ የሌላቸው ደግሞ ፕሮካርዮቲክ በመባል ይታወቃሉ፡፡ ኒውክሊየስ የሌላቸው ሴሎች ኒውክሊየስ ካላቸው ሴሎች አንፃር ሲታዩ እምብዛም ውስብስብ ስላልሆኑ ብዙዎች የእንስሳትና የአዕፅዋት ሴሎች ከባክቴሪያ ሴሎች ተሻሽለው እንደመጡ ያምናሉ፡፡
ፐሮካርዮቲክ ሴልን ከፋብሪካ ጋር ማነፃፀር ይችላል፡፡ ይህ ሴል ከአንድ ትንሽ የጤፍ ቅንጣት በብዙ መቶዎች እጥፍ ያነሰ ቢሆንም፤ ጠንካራ የሆነውና የመተጣጠፍ ባህሪይ ያለው የሴሉ ሽፋን ባዕድ ነገር ወደ ውስጥ መግባት እንዳይቻል ይከላከላል፡፡

የሴሉ ሽፋን የሚያከናውነው ተግባር ከጡብ እና ከሲሚንቶ ከተገነባ የአንድ ፋብሪካ አጥር ጋር ይመሳሰላል፡፡ ወደ 10,000 የሚጠጉ የሴል ሽፋኖች ቢነባበሩ እንኳን የሚኖራቸው ውፍረት ከአንድ ወረቀት ውፍረት አያልፍም፡፡

የሴል ሽፋን ልክ እንደ ፋብሪካ አጥር በሴሉ ውስጥ ያሉትን ነገሮች በዙሪያው ካሉ ጎጂ ነገሮች ይጠብቃቸዋል፡፡ ይህ ሽፋን እንዲህ ያለውን የመከላከል ተግባር ቢፈፅምም ድፍን ያለ ግን አይደለም፡፡ ከዚህ ይልቅ እንደ ኦክስጅን ያሉ ጥቃቅን ሞሎኪዩሎች እንዲገቡና እንዲወጡ በማድረግ ሴሉ ‹‹እንዲተነፍስ›› ያስችለዋል፡፡ ጉዳት ሊያስከትሉ የሚችሉ ውስብስብ የሆኑ ሞሎኪውሎች እንኳን ከሴሉ ፈቃድ ውጭ እንዳይገቡ ይከላከላል፡፡ በተጨማሪም ጠቃሚ የሆኑ ሞሎኪዩሎች ከሴሉ እንዳይወጡ ያደርጋል፡፡ በአጠቃላይ ፋብሪካው ወደ ውስጥ የሚገባውንም ሆነ የሚወጣውን ምርቶች የሚቆጣጠሩ ጠበቃዎች ሊኖሩት ይችላሉ ማለት ነው፤ በተመሳሳይም የሴሉ ሽፋን እንደበርና እንደጠባቂ ሆነው የሚያገለግሉ ለየት ያሉ የፕሮቲን ሞሎኪውሎች አሉት፡፡

ፕሮቲኖች የሚመረቱበት መንገድ
የፕሪካርዮቲክ ሴል ውስጠኛ ክፍል አል ምግቦችን፣ ጨዎችንና ሌሎች ንጥረ ነገሮችን በያዘ ፈሳሽ የተሞላ ነው፡፡ ሴሉ የሚያስፈልጉትን ነገሮች ለማምረት እነዚህን ንጥረ ነገሮች ይጠቀማል፡፡ ይሁን እንጂ ስራው በዘፈቀደ የሚከናወን አይደለም፡፡ ጥሩ የስራ አመራር እንዳለው ፋብሪካ ሁሉ ሴሉ በሺዎች የሚቆጠር ኬሚካላዊ ሂደቶች በተወሰነላቸው ቅደም ተከተልና በተመደበላቸው ጊዜ እንዲከናወኑ ያደራጃቸዋል፡፡

አንድ ሴል አብዛኛውን ጊዜውን የሚያሳልፈው ፕሮቲኖችን በመስራት ነው፡፡ ይህን የሚያደርገው፣ በመጀመሪያ ሴሉ 20 የሚያህሉ የተለያዩ አሚኖ አሲዶችን ሲሰራ ይታያል፤ እነዚህ አሚኖ አሲዶች ፕሮቲን ለመስራት የሚያገለግሉ መሰረታዊ ነገሮች ናቸው፡፡ ለግንባታ የሚያስፈልጉት እነዚህ መሰረታዊ ነገሮች ወደ ራይቦዘሞች ይወሰዳሉ፤ ሪይቦዘም አሚኖ አሲዶች በተወሰነላቸው ቅደም ተከተል ተጣምረው ራሱን የቻለ አንድ ፕሮቲን እንዲያስገኙ የሚያደርግ አውቶማቲክ ማሽን ነው ሊባል ይችላል፡፡ የአንድ ፋብሪካ የስራ ሂደት ማዕከላዊ በሆነ የኮምፒዩተር ፕሮግራም እንደሚመራ ሁሉ በሴል ውስጥ የሚከናወኑት ብዙዎቹ ተግባሮችም የሚመሩት ዲኤንኤ በሚባል ‹‹የኮምፒዩተር ፕሮግራም ወይም ኮድ በሚመስል አማካኝነት ነው›› ራይቦዞም የትኞቹን ፕሮቲኖች መስራት እንዳለበትና በምን አይነት መንገድ እንደሚሰራቸው የሚገልጽ ዝርዝር መመመሪያ ከዲኤንኤ ይቀበላል፡፡
ፕሮቲን ከተሰራ በኋላ የሚያከናውነው ነገር በጣም የሚያስደንቅ ነው! እያንዳንዱ ፕሮቲን ይተጣጠፍና በአይነቱ ልዩ የሆነ ባለሶስት ገና ቅርጽ ይይዛል፡፡ ፕሮቲን የሚያከናውነውን ተግባር የሚወስነው ይህ ቅርጽ ነው፡፡

ሴሎች ከሚሰሯቸው ፕሮቲኖች አንዱ ኢንዛይም ነው፡፡ እያንዳንዱ ኢንዛይም አንድን አይነት ኬሚካላዊ ሂደት ማፋጠን እንዲችል በተለየ መንገድ ይተጣጠፋል፡፡ በመቶዎች የሚቆጠሩ ኢንዛይሞች እርስ በርሳቸው ተባብረው በመስራት የሴሉን እንቅስቃሴ ይቆጣጠራሉ፡፡
አንድ ፕሮቲን በትክክል ካልተሰራና ተገቢው ቅርፅ እንዲኖረው ተደርጎ ካልተጣጠፈ የሚፈለግበትን ተግባር በተገቢው ሁኔታ ማከናወን የማይችል ከመሆኑም በላይ ሴሉ ላይ ጉት ሊያደርስ ይችላል፡፡

በሴል ውስጥ የሚመረተው እያንዳንዱ ፕሮቲን፣ የት መሄድ እንዳለበት የሚገልፅ አድራሻ አለው፡፡ በእያንዳንዱ ደቂቃ በሺ የሚቆጠሩ ፕሮቲኖች ተሰርተው ወደሚፈለጉበት ቦታ የሚደርሱ ቢሆንም አንዳቸውም እንኳን ወደ ተሳሳተ ቦታ አይሄዱም፡፡

ኢንዛይሞችን ለመስራት ዲኤንኤ ሲያስፈልግ ዲኤንኤ ለመስራት ደግሞ ኢንዛይሞች ያስፈልጋሉ፡፡ በተጨማሪም ሌሎች ፕሮቲኖች በሴል ብቻ ሊመረቱ ይችላሉ፤ ይሁን እንጂ አንድ ሴል ሊመረት የሚችለው በፕሮቲኖች ብቻ ሊሆን ይችላል፡፡

በሰው አካል ውስጥ የሚገኙ አንዳንድ ሴሎች 10,000,000,000 በሚያህሉ የፕሮቲን ሞሎኪዩሎች የተገነቡ ሲሆን እነዚህ ሞሊኪዩሎች አይነታቸው በመቶ ሺ የሚቆጠር ሊሆን ይችላል፡፡

ሴሎች በምን ያህል ፍጥነት ይባዛሉ?

አንዳንድ ባክቴሪያዎች በ20 ደቂቃ ውስጥ ራሳቸውን መተካት ይችላሉ፡፡ እያንዳንዱ ሴል ዋናውን የኮምፒዩተር ፕሮግራም ከገለበጠ በኋላ ለሁለት ይከፈላል፡፡ የማያቋርጥ ኃይል ካገኘ አንድ ሴል ብቻ እንኳ በከፍተኛ ፍጥነት ሊበዛ ይችላል፡፡ በዚህ ፍጥነት ቢበዛ በሁለት ቀን ውስጥ ብቻ ቁጥሩ በጣም በዝቶ ክብደቱ ከምድር ክብደት 2,500 ጊዜ በላይ ሊበልጥ ይችላል፡፡ ይበልጥ ውስብስብ የሆኑ ሴሎችም በፍጥነት መበዛዘት ይችላሉ፡፡ ለምሳሌ በእናታችን ማህፀን ውስጥ በነበርንበት ጊዜ የአንጎላችን ሴሎች በከፍተኛ ፍጥነት በመባዛት በደቂቃ 250,000 ያህል ሴሎችን ይሰሩ ነበር፡፡

የዲ.ኤን.ኤ ሞሎኪዩል በተደጋጋሚ ጊዜያት እንደሚነበብና እንደሚባዛ መፅሐፍ ነው፡፡ በአንድ ሰው አማካይ ዕድሜ ውስጥ ዲ.ኤን.ኤ ፈጽሞ እንከን በማይወጣለት መንገድ ወደ 10,000,000,000,000,000 ለሚጠጋ ጊዜ ይባዛል፡፡

አንድ ግራም ዲ.ኤን.ኤ አንድ ትሪሊዮን ሲዲዎች ሊይዙ የሚችሉትን ያህል መረጃ መያዝ ይችላል፡፡

የኢትዮጵያ ርዕዮት ተናገረች

$
0
0

ከፕሮፌሰር አለማየሁ ገብረማርያም
ትርጉም በነጻነት ለሀገሬ

አይበገሬዋ ጀግናዋ ርዕዮት!

በንጹሀን ዜጎች ላይ ስቃይን በመፈጸም ከሚታወቀውና ከአዲስ አበባ ከተማ እምብርት በስተደቡብ ምስራቅ ተንጣሎ ከሚገኘው እና በተለምዶ ቃሊቲ እየተባለ ከሚጠራው የመለስ ዜናዊ የማጎሪያ እስር ቤት (የኢትዮጵያ “ሮቤን ደሴት” ማለትም ነልሶን ማንደላ የታሰሩበት) ባልተጠበቀ ጊዜ የተለቀቀችው ጀግናዋ ርዕዮት ዓለሙ ከማጎሪያው እስር ቤት በወጣች በሰዓታት ጊዜ ውስጥ ለአሜሪካ ድምጽ የአማርኛው አገልግሎት ቃለ መጠይቅ ሰጠች፡፡

reyot
ዴሞክራሲ እና ፍትህ የሰፈኑባት ኢትዮጵያ እውን እስከምትሆን ድረስ ሙሉ በሙሉ ትግሌን እቀጥላለሁ፡፡ እንደዚህ የሆነች ኢትዮጵያን እስከማይ ድረስ ትግሌን በተጠናከረ መልኩ እቀጥላለሁ በማለት የዓላማ ጽናቷን በድጋሜ አረጋግጣለች፡፡

ርዕዮት በአምባገነኑ ገዥ አካል የ14 ዓመታት እስር ተበይኖባት ይህ እስር እንደገና ወደ 5 ዓመታት ከተቀየረ በኋላ 4 ዓመታት ከ17 ቀናት (1480 ቀናትን) በእስር ቤት አሳልፋለች፡፡

አሁን በህይወት በሌለው በመለስ ዜናዊ እና በእርሱ ወሮበላ የዘራፊ ቡድን ስብስብ በህዝባዊ ወያኔ ሀርነት ትግራይ (ህወሀት) የጸረ ሽብር ሕግ እየተባለ በሚጠራው ሰላማዊ ዜጎችን የማጥቂያ መሳሪያ የፈጠራ እና የሸፍጥ ክስ ተመስርቶባት ነበር ወደ ዘብጥያ የተወረወረችው፡፡

ታላቁ መሪ ኔልሰን ማንዴላ ለዘረኛው የጥቂት ነጮች ፈለጭ ቆራጭ አምባገነን ስርዓት ጭቆና አራማጆች እንዲህ የሚል ማስጠንቀቂያ ሰጥተው ነበር፣ “በማዘግየት በኩል ውጤታማ ልትሆኑ ትችላላችሁ፣ ሆኖም ግን ደቡብ አፍሪካ ወደ ዴሞክራሲ የምታደርገውን ሽግግር በምንም ዓይነት መልኩ በፍጹም ልታስቀሩት አትችሉም፡፡“

የርዕዮት ዋናው መልዕክት ማጠንጠኛውም ይኸው በታላቁ መሪ በኔልሰን ማንዴላ የተነገረው የአፓርተይድ ዓይነት ወሮበላ የዘራፊ አምባገነን ቡድን ስብስብ ለሆነው ለወያኔ ትክክለኛ የሆነ ገላጭ ድርጊት ነው፡፡ “ዴሞክራሲ እና ፍትህ የሰፈኑባት ኢትዮጵያ እውን እስከምትሆን ድረስ ሙሉ በሙሉ ትግሌን እቀጥላለሁ፡፡” ነው ያለችው፡፡

ትግሉ ይቀጥላል!

ማንዴላ ከዚህ በተጨማሪም እንዲህ ብለው ነበር፣ “እስር ቤት እራሱ ትዕግስትን እና ጽናትን የሚያላብስ ተዝቆ የማያልቅ ትምህርት የሚሰጥ ተቋም ነው፡፡ ከሁሉም በላይ ደግሞ የአንድን ሰው የአድራጊነት እና የመፈጸም ችሎታ የሚመዝን ፈተና ነው፡፡“

ርዕዮት እ.ኤ.አ ሀምሌ 9/2015 ከመለስ ዜናዊ የማጎሪያ እስር ቤት በመውጣት በኢትዮጵያ ለዴሞክራሲ እና ለፍትህ መስፈን ያላትን ለድርድር የማይቀርበውን ቁርጠኛ የሆነውን የዓላማ ጽናቷን በተግባር አረጋግጣለች፡፡ ይህንን ያደረግችው ግን እንዲሁ ከምንም ሳይሆን ከፍተኛ የሆነ ዋጋ ከፍላ ነው፡፡

ለአራት ዓመታት እና ለ17 ቀናት ርዕዮት በመለስ ዜናዊ የማጎሪያ እስር ቤት በየዕለቱ ውርደት፣ ለብቻ ተነጥሎ መታሰር፣ ዝቅተኛ አድርጎ የመመልከት እና ከሰብአዊነት የወረደ አስቀያሚ ድርጊት ይፈጸምባት ነበር፡፡

ሆኖም ግን ጀግናዋ ርዕዮት ሁሉንም ነገር በጽናት ተቋቁማዋለች፡፡

ለአራት ዓመታት እና ለ17 ቀናት ርዕዮት በአምባገነኑ የመለስ ዜናዊ የማጎሪያ እስር ቤት የበቀል እና የሰይጣናዊ ጥላቻ መፈጸሚያ ከርስ ውስጥ ምርኮኛ ሆና ቆይታለች፡፡

በማጎሪያው እስር ቤት ውስጥ እጅግ በጣም አስቀያሚ የሆነውን የሰብአዊ መብት ድፍጠጣ እና ከህግ አግባብ ውጭ በሆነው አያያዝ የሚፈጸምባትን ስቃይ እየገለጸች ድምጿን ከፍ አድርጋ ስታሰማ ቆይታለች፡፡

ታጋሽ ሆናም በጽናት ቆይታለች፡፡

ለአራት ዓመታት እና ለ17 ቀናት ርዕዮት በመለስ ዜናዊ የማጎሪያ እስር ቤት ውስጥ ጭንቅላቷ እየደማ ሆኖም ግን ለአንዲት ቅንጣት ሰከንድ እንኳ ለአምባገነኖች ሳታጎበድድ በጽናት ግዳጇን የተወጣች ጀግኒት ናት፡፡

ርዕዮት እንደ አረብ ብረት እየጠነከረች የመጣች ጀግኒት ናት!!!

ርዕዮት በአምባገነኑ የመለስ ዜናዊ የማጎሪያ እስር ቤት ለዓመታት ስቃይ እና ግፍ ስትቀበል ቆይታለች፡፡ ሆኖም ግን ምንም ዓይነት ፍርሀት ሳይጎበኛት በጽናት ቆይታለች፡፡

ጀግኒቱ ምንም ዓይነት ፍርኃት የለባትም ምክንያቱም ርዕዮት የዕጣ ፈንታዋ እመቤት ባለቤት እና የነብሷ መርከብ ካፒቴን ሌላ ማንም ወሮበላ ዘራፊ ሳይሆን እራሷ ናትና፡፡

ታዋቂው ገጣሚ ዊሊያም ኢርነስት ሄንለይ ከበርካታ ዓመታት በፊት “የማይበገሩ ጀግኖች” በሚል ርዕስ እንዲህ የሚሉ የግጥም ስንኞችን የቋጠሩት ለካስ ለእነ ርዕዮት ዓለሙ፣ እስክንድር ነጋ፣ ውብሸት ታዬ፣ ተመስገን ደሳለኝ፣ አብርሃ ደስታ፣ ለዞን 9 ጦማሪያን እና እንደ እነርሱ ላሉት ለሌሎች ጀግና የፖለቲካ እስረኞች ኖሯል፡

ጋርዶኝ ከነበረው ድቅድቁ ጨለማ፣
ጥልቀትን ከያዘው ከጉድጓዱ ወማ፣
ጥቁር ከለበሰው የመሬት ውስጥ ካስማ፣
አሻግሮ ከያዘው የምድር ላይ ማማ፡፡

ገብቸ በመሀል ሳንድዊች ተደርጌ፣
ባልፈጸምኩት ጥፋት ተጥዬ ከግርጌ፣
ሀበሳ ግፍ አየሁ ከጨቋኝ በርግጌ፡፡

እናም ፈጣሪዬን አምላኬን ላመስግን፣
ለመንፈሴ ጽናት ለሰጠኝ ብርታቱን፣
ከወገኔ ፍቅር እንዳይ በረከቱን፣
ግፍን ለማስወገድ ለመስበር መርገምቱን፡፡

በግፈኞች መዳፍ ስደቆስ ታፍኘ፣
ያለፍትህ አካል መጫወቻ ሆኘ፤
የይስሙላ ዳኛ መጨፈሪያ ሆኘ፡፡

አጥቸ ፍርድ ቤት፣
አቤት የምልበት፣
ፍትህ የማይበት፣
ግፍ የሚመታበት፡፡

ፍትህ ካደባባይ ከመንበሩ ጠፍቶ፣
አምባገነን ነግሶ ስርዓቱ ከርፍቶ፣
ህዝብን አተራምሶ ሀገርን አራቁቶ፣
ዜጋን አሰድዶ ወገን አስከፍቶ፣
በህዝቦች ጫንቃ ላይ ገኖ ተንሰራፍቶ፣
ለዘላለም ሊኖር ሁሉንም አጥፍቶ፣
በተንኮል በደባው ምሎ ተገዝቶ፣
አልሞ ተነስቷል ንጉስ ሊሆን ከቶ፡፡

ለማይበገረው ጠንካራው መንፈሴ፣
አምላክን ለመስግን በመርካቷ ነብሴ፡፡

በግፈኞች መዳፍ በወጥመድ ብወድቅም፣
ሰብአዊነት ክብሬ ቢጣስ ቢረገጥም፣
ብሩሁ አእምሮዬ አካሌ ቢቆስልም፣
ስሜንም ቢያጎድፉት ጥላሸት ቢቀቡም፣
ከዓላማዬ ጽናት አንዲት ጋት አልሸሽም፣
ግርፋት ስቃዩ ጡጫው ቢጨምርም፣
እራሴ ቢደማም አልተንበረከኩም፣
ተሰቃየሁ ብዬ አላፈገፍግም፣
ለጨቋኞች ደስታ አላጎበድድም፡፡

ከዚህ በላይ በቀል አድልኦ ጥላቻ፣
ስምን የማጠልሸት የሰይጣን ዘመቻ፣
ይፈጸማል እኮ በዕኩዮች ሽኩቻ፡፡

እናም የዘመናት ስቃይ ይቀጥላል፣
እኔን ግን መንፈሴ ቆራጥ ያደርገኛል፣
የወገኔ ፍቅር ያንገበግበኛል፡፡

ከምንጊዜም በላይ በሩ ቢጣመምም፣
የተንሸዋረረው ፍትህ ቢጓደልም፣
በኔ ላይ ደጋግሞ ቅጣት ቢቆልልም፣
ከዓላማዬ ፍንክች በፍጹም አልልም፡፡

የእራሴ እጣፈንታ ወሳኙ እራሴ ነኝ፣
ማንም አምባገነን የማይጨፍርብኝ፣
በዲያብሎስ መንገድ የማያስገድደኝ፣
የነብሴ መርከቡ ካፕቴኑ እራሴ ነኝ፡፡

አራቱ የዞን 9 ጦማሪያን ባስቸኳይ ይፈቱ፣

የወያኔ ወሮበላ የዘራፊ ቡድን ስብስብ ገዥ አካል 5 ወጣት ጦማሪያንን እና ጋዜጠኞችን የህግ አማካሪዎቻቸው፣ እራሳቸው ግፉ የተፈጸመባቸው እና ወላጆቻቸውም ሳይቀር ምንም ነገር ሳያውቁ ባልተጠበቀ ሁኔታ በድንገት ከመለስ ዜናዊ የማጎሪያው እስር ቤቱ ለቋቸዋል፡፡ ከሕግ አግባብ ውጭ በዘፈቀደ ከአንድ ዓመት በላይ በእስር ቤት ሲማቅቁ ቆይተዋል፡፡ ዴሞክራሲ እና ፍትህ በዓለም ላይ ሁሉ በአደባባይ እየሰፈነ እና እየለመለመ ባለበት በአሁኑ ጊዜ በማጎሪያ እስር ቤት አስገብቶ እንደ እባብ የሚቀጠቅጥ፣ በንጹሀን ዜጎች ህይወት ላይ ቁማር የሚጫወት እና እንደፈለገ ወስዶ እንደ ጥጃ የሚያስርና የሚፈታ የዘራፊ ወሮበላ ቡድን ስብስብ በ21ኛው ክፍለ ዘመን ኢትዮጵያ መታየቱ እጅግ ያሳዝናል፡፡ እነዚህ ንጹሀን ዜጎች በወጡባት እግራቸው ነገም ተመልሰው የማይገበቡት ምን ዋስትና ሊኖር ይችላል! ምንም፡፡

የጋዜጠኞች ተከላካይ ኮሚቴ (ጋተኮ) “የኢትዮጵያ መንግስት ባለስልጣኖች የዞን 9 ጦማሪያንን ከሰብአዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች ጋር በመስራት እና የማህበራዊ የግንኙነት መስመሮችን በመጠቀም በኢትዮጵያ ውስጥ አለመረጋጋት እንዲፈጠር በመስራት ላይ ናቸው:: ቡድኑ በኢትዮጵያ ስላለው የፖለቲካ ጭቆና እና ማህበራዊ የፍትህ መጓደል ሲጽፍ የነበረ ሲሆን የእነዚህ ጦማሪያን ድረ ገጾች በሀገሪቱ ውስጥ በየጊዜው ይታፈኑ ነበር፡፡” በማለት ስለተናገረው ስለዞን 9 ጦማሪያን ነው እየጻፍኩ ያለሁት፡፡

እ.ኤ.አ ሀምሌ 8/2015 የወያኔ ወሮበላ የዘራፊ ቡድን ስብስብ ገዥ አካል ሁሉንም የውንጀላ ክሶች በመጣል ባልታሰበ ሁኔታ ጦማሪያኑን እና ጋዜጠኞችን ከመለስ ዜናዊ የማጎሪያ እስር ቤት ለቋቸዋል፡፡

እስረኞቹ ለሌሎቹ ከአንድ ዓመት በላይ በግፍ ታስረው በመማቀቅ ላይ ለሚገኙት ንጹሀን ወገኖቻቸው እና ጓደኞቻቸው እንኳ በሉ ደህና ሁኑ ለማለት ጊዜ አላገኙም ነበር፡፡

ከማጎሪያው እስር ቤት የወጡት ጦማሪያን እና ጋዜጠኞች የሚከተሉትን ያካትታል፡ ዘላለም ክብረት፣ ማህሌት ፋንታሁን፣ ተስፋለም ወልደየስ፣ አስማማው ኃ/ጊዮርጊስ እና ኤዶም ካሳዬ ናቸው፡፡

ከማጎሪያው እስር ቤት የተፈቱት ጦማሪያን እና ጋዜጠኞች ከእነርሱ ጋር በተመሳሳይ የፈጠራ ክስ ተመስርቶባቸው በማጎሪያው እስር ቤት የሚገኙት ሌሎች አራት ጓደኞቻቸው ለምን እንዳልተፈቱ ያሳሰባቸው መሆኑን እና የእነርሱ መፈታት ምሉዕ ደስታ ያልሰጣቸው መሆኑን ለህዝብ ግልጽ አድርገዋል፡፡ ደህና፣ እንግዲህ የወያኔ ወሮበላ የዘራፊ ቡድን ስብስብ የይስሙላው የዝንጀሮ ፍርድ ቤት ሚስጥራዊ እንቆቅልሽ እዚህ ላይ ነው፡፡ በተመሳሳይ ውንጀላ ያሰራቸውን ዜጎች እውነት ባይሆንም እንኳ ተመሳሳይ ፍትህ የማይሰጥ በፖለቲካ ቡድኑ የሚጦዝ ድሁር የፍትህ አካል መሆኑን በግልጽ ያመላክታል፡፡

ኢትዮጵያ ርዕዮት ዓለሙን የመሰለች ጀግኒት አለቻት፣

ሁሉም ሀገሮች ከጊዜ ወደ ጊዜ በሚፈጠሩ ጀግኒቶች እና ጀግኖች በመታደል ላይ ናቸው፡፡

አሜሪካ በርካታ ጀግኖች እና ጥቂት ጀግኒቶች አሏት፡፡ አብዛኞቹ የአሜሪካ ጀግኒቶች ያልተዘመረላቸው ናቸው፡፡

አሜሪካዊት ጀግኒት ሐሪዬት ቱብማን እ.ኤ.አ በ1950ዎቹ ባሮች ነጻነታቸውን እንዲቀዳጁ በማሰብ “የምድር ስር ባቡር” ማለትም ከባርነት ወደ ነፃነት ለመጥፋት የሚሞክሩትን የባርነት ተገዢዎች ህቡዕ በሆነ መልኩ በማደራጀት እና በማስተባበር የስብሰባ ቦታዎችን፣ የሚስጥር መንገዶችን፣ በመጓጓዣ ቦታዎች እና በሰላማዊ የህዝብ መኖሪያ ቤቶች በመጠቀም ትግሉ በተጠናከረ መልኩ እንዲካሄድ ጥረት ሲያደርጉ ነበር፡፡

እ.ኤ.አ በ1870ዎቹ የመጀመሪያዎቹ ዓመታት አካባቢ ሱሳን ቢ.አንቶኒ የአሜሪካ ሴቶች የመምረጥ፣ የንብረት የባለቤትነት መብት እና ከዚህም በላይ በመሄድ የሰራተኞች ማህበር አባል እንዲሆኑ የሚያስችሏቸውን መብቶቻቸውን ለማስከበር አመራር ይሰጡ የነበሩ ጀግኒት ሴት ነበሩ፡፡

የዩናይትድ ስቴትስ ምክር ቤት “የሲቪል መብቶች ተከራካሪ የመጀመሪያዋ አመቤት” እና እ.ኤ.አ በ1950ዎቹ አጋማሽ የአሜሪካ የሲቪል መብቶች ንቅናቄ እናት እያለ የሚጠራቸው ሮሳ ፓርክስ ቀላል የሆነውን ህዝባዊ እምቢተኝነትን እንደ ትግል ስልት በመጠቀም ለነጻነት፣ ለእኩልነት እና ለፍትህ ሲካሄድ የነበረውን ትግል አቀጣጥለዋል፡፡ ከፊት ለፊት የተቀመጠችበትን የአወቶብስ መቀመጫ እንድትለቅ እና ወደ ኋላ ሄዳ እንድትቀመጥ የሚያዝዘውን የጨቋኞች ትዕዛዝ አሻፈረኝ፣ እምቢ በማለት ለሴቶች መብት መከበር ስትል የመጀመሪያዋ ሆናለች፡፡

ይህች ጀግኒት እንዲህ ብላ ነበር፣ “የለም፣ በፍጹም ከዚህ መቀመጫ አልንቀሳቀስም!“ በማለት ዜጎችን በጾታ ለሚከፋፍለው ሸውራራ የፖሊስ እና የፍትህ ስርዓት በአደባባይ በግልጽ ተናግራለች፡፡

በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ አፍሪካ አሜሪካውያን ወዲያውኑ ትግሉን በመቀላቀል ከመብት ታጋዩዋ ጋር አብረው መዘመር ጀመሩ፡፡

“የትም አንንቀሳቀስም!/ልክ በውኃ አጠገብ እንደቆመ ዛፍ/ ህብረት ከእኛ ጎን ነው የተሰለፈው/እኛ ለነጻነታችን እንታገላለን/ ለልጆቻችን ስንል እንታገላለን/ ጠንካራ የሆነ ማህበር እንመሰርታለን/ጥቁሮች እና ነጮች በአንድነት ሆነን/ወጣቶች እና አዛውንቶች በአንድ ላይ በመቆም/ የትም አንንቀሳቀስም፣ የትም፡፡“

የአፍሪካ አሜሪካዊ ሴቶች ለሲቪል መብቶች እንቅስቃሴ ትግል ዋና የጀርባ አጥንት ነበሩ፡፡ ሆኖም ግን ያልተዘመረላቸው ጀግኖቶች ናቸው፡፡

የዘመናዊ ሰብአዊ መብቶች ንቅናቄ እናት የሆኑት ኢሊኖር ሩዝቬልት ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት ፍጻሜ በኋላ ለሰብአዊ መብቶች ስምምነት መሰረት የሆነውን የዓለም አቀፉን የሰብአዊ መብት ድንጋጌ በማርቀቁ ሂደት ከፍተኛ ኃላፊነትን ይዘው የነበሩ ብቸኛዋ ሴት ነበሩ፡፡

በእኔ አመለካከት ርዕዮት ዓለሙ የዚህ ዓይነት አብዮተኞች ቡድን አባል ናት ማለት እችላለሁ፡፡ እንደዚህ ያሉት ለፍትህ፣ ለእኩልነት፣ ለሲቪል እና ሰለብአዊ መብቶች ዓይናቸውን ሳያራግቡ በመንፈሰ ጠንካራነት ታሪክን የሚለውጡ ደፋር፣ በአመክንዮ የሚያምኑ እና ለህዝብ ሲሉ መስዋዕትነትን ለመክፈል ዝግጁ የሆኑ ሴቶች ናቸው፡፡

እውነት ተናጋሪዋ፣

ርዕዮት “የኢትዮጵያ እውነት ተናጋረዊ ሴት” በመባል ትጠራለች፡፡

ዘመናዊው የአፍሪካ ታሪክ በሚጻፍበት ጊዜ እና በአፍሪካ አዳራሽ የዝነኞች ስም ዝርዝር ከአፍሪካ አዳራሽ ተዋራጆች ስም ዝርዝር ተለይቶ ሲጻፍ የርዕዮት ስም “በእሳት ውስጥ ተፈትነው ያለፉ” ከሚለው ከጀግኖቹ የክብር ስም ዝርዝር ውስጥ በግንባር ቀደምትነት የሚጻፍ ይሆናል፡፡

ርዕዮት ዓለሙ አራት ዓመታት ከ17 ቀናት በቆየው ጊዜ ውስጥ የመለስ ዜናዊን የገኃነም ቅጣት ተጋፍጣለች፡፡

እ.ኤ.አ ሀምሌ 9/2015 ወጣት የሆነችዋ የአረብ ብረቷ ሴት ከመለስ ዜናዊ የማጎሪያ እስር ቤት በመውጣት ለዓለም ህዝብ እንዲህ በማለት አውጃለች፡

ዴሞክራሲ እና ፍትህ የሰፈኑባት ኢትዮጵያ እውን እስከምትሆን ድረስ ሙሉ በሙሉ ትግሌን እቀጥላለሁ፡፡ እንደዚህ የሆነች ኢትዮጵያን እስከማይ ድረስ ትግሌን በተጠናከረ መልኩ እቀጥላለሁ፡፡

የወያኔ ወሮበላ የዘራፊ ቡድን ስብስብ አገዛዝ እርሷን በቁጥጥሩ ስር አድርጎ በጉልበቷ እንድትንበረከክ ለማድረግ ያልፈነቀለው ድንጋይ ያልቧጠጠው አቀበት አልነበረም፡፡

የስነ ልቦና ስብራት ለማድረስ እና ያላትን ጠንካራ ተስፋ ለማዳፈን ለብቻዋ ለይቶ በአንድ ክፍል ውስጥ እንድትታሰር አደረገ፡፡

ለህይወት አስጊ በሆነ በሽታ ተይዛ በነበረበት ጊዜ ህክምና እንዳታገኝ አበርትቶ ሰርቷል፡፡

ሴትነቷን እና ሰብአዊ ፍጡር መሆኗን ክደው ተንቀሳቅሰዋል፡፡

መንፈሷን ለመግደል የሞት ሽረት ትግል አድርገዋል፡፡

የመለስ ዜናዊ የማጎሪያ እስር ቤት በመባል በሚታወቀው እስር ቤት የጥላቻ እና የበቀል ቦታ ማድረግ የሚችሉትን ሁሉ አድርገዋል፡፡

ሆኖም ግን በምንም ዓይነት መልኩ የርዕዮትን ቅስም መስበር ሳይቻላቸው ቀርቷል፡፡

አዕምሯዋን መቆጣጠር አልቻሉም፡፡

መንፈሷን መስበር አልቻሉም፡፡

ለመኖር ያላትን ምኞት ማጥፋት ሳይቻላቸው ቀርቷል፡፡

በኩራት ደረቷን ነፍታ በመቆም ለዓለም እንዲህ ትላለች፡

ዴሞክራሲ እና ፍትህ የሰፈኑባት ኢትዮጵያ እውን እስከምትሆን ድረስ ሙሉ በሙሉ ትግሌን እቀጥላለሁ፡፡ እንደዚህ የሆነች ኢትዮጵያን እስከማይ ድረስ ትግሌን በተጠናከረ መልኩ እቀጥላለሁ፡፡

የወያኔ ወሮበላ የዘራፊ ቡድን ስብስብ አሳሪዎቿ ከመለስ ዜናዊ የማጎሪያ እስር ቤት እንድትወጣ ከማድረጋቸው ከደቂቃዎች በፊት አሁን እንዳለችው እንደምትሆን ነግራቸዋለች፡፡ ከማጎሪያው እስር ቤት እንድትወጣ አይፈቅዱላትም ምክንያቱም ከአራት ዓመታት በፊት ታደርግ እንደነበረው ሁሉ አሁንም ትግሏን እንደምትቀጥል ያውቃሉና፡፡

ርዕዮት የወያኔ ወሮበላ የዘራፊ ቡድን ስብስብን እንዲህ በማለት አስጠንቅቃለች፣ “ባላጠፋሁት ጥፋት ምንም ዓይነት ይቅርታ ሳልጠይቅ ከማጎሪያው እስር ቤት ወጣሁ ብዬ ለህዝብ ስናገር መልሳችሁ ወደ ማጎሪያው እስር ቤት ልታመጡኝ ትችላላችሁ፣ እኔ ግን በዓላማዬ ጸንቼ እቆያለሁ፡፡ ስለእኔ ከእስር መፈታት ሀሰት ብትናገሩ እውነቱን ለህዝብ ይፋ አደርጋለሁ እናገራለሁ፡፡“

በተለያዩ በርካታ አጋጣሚዎች የርዕዮት አሳሪዎች ይቅርታ ጠይቃ ነጻ ሆና እንድትወጣ የምትፈርምበትን ፎርም እያዘጋጁ ፈርሚ እያሉ በተደጋጋሚ ለምነዋታል፡፡

እርሷግን ወረቀቱን ወስዳ እንደምትጥለው ነግራቸዋለች፡፡

“ብረቷ ወይዘሮ ” እየተባለች እንደምትጠራው የንግሊዝ ጠቅላይ ሚኒስትር ማጊ ታቼር በህይወት ብትኖር ኖሮ እንዲህ እላት ነበር፣ “ማጊ እባክሽን ወደ ጎን ሁኝ፣ ቦታውን ለርዕዮት ልቀቂ!“

ርዕዮትን እና ሌሎችን ጦማሪያን እና ጋዜጠኞችን የፈቷቸው ለምንድን ነው?

የወያኔ ወሮበላ የዘራፊ ቡድን ስብስብ ርዕዮት ለፍትህ ወይም ደግሞ ስለእርሷ የልብ ሀዘን መናገር እንድትችል እኔንም ጨምሮ አይፈቅዱላትም ምክንያቱም ተጻራሪ በሆነ መልኩ እነርሱ የሚያዝኑበት ልብም ሆነ መልካም ነገር የላቸውምና፡፡

ርዕዮት ከእስር ቤት ወጥታ ስትሄድ ጥርሳቸውን እንደሚነክሱ እና የሆድ ቁርጠት እንደሚይዛቸው ጥርጥር የለውም፡፡ ቢቻላቸው ኖሮ እርሷ በክፉ በሽታ ምክንያት ህይወቷ አልፏል በማለት ለዓለም ህዝብ ማሳወቅን ይመርጡ ነበር፡፡ በዚህ ጊዜ ግን ዕድል ከወያኔ ወሮበላ የዘራፊ ቡድን ስብስብ ጋር አይደለችም፡፡

ይህንን ድርጊት ያደረጉት ለግንባር መሸፈኛ እና በዚህ ወር የሚመጡትን የኦባማን ልብ ለመማረክ ታስቦ የተደረገ ነው፡፡

ይህንን በማድረግ ለኦባማ ጥሩ ነገር እየሰሩ እንዳሉ ለማስመሰል የተደረገ የቅጥፈት ተውኔት ነው፡፡ የኦባማ ጉብኝት ርዕዮትን እና ሌሎችን የታሰሩ ጋዜጠኞች እና የፖለቲካ እስረኞችን ለመጠየቅ ከሆነ የሚፈልጉት ነገር አይደለም፡፡

ኦባማ ለሚከተሉት ጥያቄዎች ምላሽ እንደሚሰጡ እናስብ፡ “ክቡር ፕሬዚዳንት ወደ መለስ ዜናዊ የማጎሪያ እስር ቤት በመሄድ የእርስዎን መሄድ የሚጠባበቁትን እና በግፍ በእስር ላይ እየማቀቁ የሚገኙትን እስክንድር ነጋን፣ ርዕዮት ዓለሙን፣ ውብሸት ታዬን፣ ተመስገን ደሳለኝን፣ የዞን 9 ጦማሪያንን እና በሺዎች የሚቆጠሩትን ሌሎችን የፖለቲካ እስረኞች ሊጎበኙ ይችላሉን? በደርዘን በሚቆጠሩ ኪሎ ሜትሮች ርቀት ላይ ይገኛሉ፡፡ እባክዎትን ሄደው ለመጎብኘት ይችላሉን?“

የወያኔ ወሮበላ የዘራፊ ቡድን ስብስብ በልካቸው የተሰፋ የማስመሰያ ልብስን በመልበስ ዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብት ተከራካሪ ድርጅቶች በተደጋጋሚ እንደሚሉት የሰው ልጆችን መብት በመጣስ ታላቅ እና አስቀያሚ ሰይጣኖች ናቸው የሚሉትን በመተው ኦባማ ይኸ መንግስት እንደሚባለው አይደለም ብለው እምነት እንዲያድርባቸው ለማድረግ ተዘየደ የሸፍጥ ስራ ነው፡፡ ከልብ እና ከፍቅር ያለመሆኑን አይደለም የኢትዮጵያ ህዝብ ይቅርና የዓለም ህዝብም አሳምሮ እንደሚያውቀው ጥርጥር የለውም፡፡

አይዟችሁ የወያኔ ወሮበላ የዘራፊ ቡድን ምንም መጨነቅ አያስፈልግም፡፡

የወያኔ ወሮበላ የዘራፊ ቡድን ስብስብ ጠባቂ መላዕክት አሏቸው – ሱሳን ራይስ እና ዌንዲ ሸርማን በኦባማ ጉብኝት ሁሉ እየተከታተሉ የሚከላከሉላችሁ መላዕክት ናቸው፡፡ ወታደራዊ ማነጻጸሪያ ቃል በመጠቀም እናንተን ለመጠበቅ በቁጥር 1 በተጠንቀቅ ላይ ይገኛሉ፡፡ ሶስት ቢራቢሮ የሚመስሉ ፍጡሮች የወያኔ ወሮበላ የዘራፊ ቡድን ስብስብ አናት ላይ እያንዣበቡ በመዞር ይጠብቋችኋል ጠንቅቃቺሁ ተመልከቱ ፡፡

ርዕዮት በፍጹም ብቻዋን አልነበረችም፣

ርዕዮት ዓለሙ በመለስ ዜናዊ የማጎሪያ እስር ቤት ለአራት ዓመታት ከ17 ቀናት በፍጹም ብቻዋን አልነበረችም፡፡

ከቤተሰቦቿ፣ ከጓደኞቿ እና ከዘመዶቿ ተለይታ ቆይታለች፡፡

እናት እና አባቷ ብቻ እንዲያዩዋት ተፈቅዶ ነበር፡፡ (የእርሷ አባት ከሆኑት እና በተጨማሪም የሕግ አማካሪ ጠበቃዋ ከሆኑት አባቷ ጋር እንኳ የሕግ ምክር ውይይት እንዲያደርጉ አየፈቀድላትም ነበር፡፡)

ቢሆንም ግን ርዕዮት በፍጹም ብቻዋን አልነበረችም፡፡

እርሷን የሚወዷት እና የሚደግፏት በዓለም ዙሪያ ሁሉ በሺዎች የሚጠቆሩ ሰዎች አሉ፡፡ እነዚህ ሰዎች ለሁልጊዜ በአዕምሯቸው እና በመንፈሳቸው ከእርሷ ጋር ነበሩ፡፡

በፌስቡክ ድረ ገጽ እና በማህበራዊ የመስመር የግንኙነት ዘዴዎች አማካይነት የሚጽፉላት ወጣት እና ቁጡ የሆኑ ወገኖች አሏት፡፡

በምንም ዓይነት መልኩ በፍጹም ብቻዋን አልነበረችም፡፡

ታላቅ ክብርን ለሚያጎናጽፉ ዓለም አቀፍ የፕሬስ ድርጅቶች ተሸላሚ እንድትሆን ስሟን በጥቆማ የሚሰጡ በርካታ ወገኖች ነበሩ፡፡

በፍጹም ብቻዋን አልነበረችም፡፡

ሌሎችም ለቁጥር የሚያዳግቱ እንደ እኔ ያሉ የእርሷን እና ሁሉንም በወያኔ እስር ቤት በመማቀቅ ላይ ለሚገኙት የኢትዮጵያ ጋዜጠኞች እና ጀግኖች የማይበገሩትን የእስክንድር ነጋን፣ ዉብሸት ታዬን፣ ተመስገን ደሳለኝን፣ አብርሃ ደስታን፣ የዞን 9 ጦማሪያንን እና እንደ እነርሱ ያሉትን ሌሎች የፖለቲካ እስረኞችን ጉዳይ የእራሳቸው የግል ተልዕኮ አድርገው የሚከታተሉ ወገኖች ነበሩ፡፡

ባገኘሁት አጋጣሚ ሁሉ በዓለም አቀፉ ማህበረሰብ የህሊና ፍርድ አደባባይ በመቆም ስለ ርዕዮት ጥብቅና ቆሜ ስሟገት ታላቅ ክብር ይሰማኛል፡፡

በርዕዮት ጉዳይ ላይ በተለይም ወይም ደግሞ በኢትዮጵያ ጋዜጠኞች እና በአጠቃላይ በሰው ልጆች ላይ በወያኔው አምባገነን ገዥ አካል ስለሚፈጸመው ወንጀል በርካታ ትችትችን ጽፊያለሁ፡፡

እ.ኤ.አ ግንቦት 2012 “ርዕዮት ዓለሙ፡ የኢትዮጵያ ፕሬስ ነጻነት ወጣቷ ጀግኒት“ በሚል ርዕስ አቅርቤው በነበረው ትችቴ ላይ ርዕዮት ለምን እንደታሰረች ግልጽ አድርጌ ነበር፡፡

ርዕዮት እና ከእርሷ ጋር እንዲከላከል የተያዘው ውብሸት ታዬ እ.ኤ.አ ሰኔ 2011 በቁጥጥር ስር ውለው በስልክ እና በኤሌክትሪክ መስመሮች ላይ አደጋ ለመጣል የሚል የፈጠራ ክስ በወያኔው ስብስብ የሀሰት ውንጀላ ተፈብሮኮ ወደ መለስ የማጎሪያ እስር ቤት እንዲወረወሩ ተደረገ፡፡ ለወራት ያህል ምንም ዓይነት ግንኙነት ሳይኖር በእስር ቤት ታጉረው ቆዩ፡፡ ሌላው ቀርቶ የግፍ ሰለባዎችን የሕግ ጠበቃዎች እንኳ እንዲጎበኟቸው አይፈቀድም ነበር፡፡

ርዕዮት በቁጥጥር ስር ለመዋሏ ትክክለኛው ምክንያት በዚያው ዓመት ሰኔ 17 በወጣ ፍትህ እየተባለ ይጠራ በነበረው እና በተከታታይ ከህትመት ውጭ ሆኖ በታገደው ሳምንታዊ መጽሔት ላይ ጽፋ ባወጣችው ጽሁፍ ነበር፡፡

በዚያ ባወጣችወ ጽሁፏ ላይ ርዕዮት አሁን በህይወት የሌለውን አምባገነኑን መለስ ዜናዊን ታላቁ የሕዳሴ ግድብ እየተባለ ሌት ቀን ስለሚደሰኮርለት የቅንጦት ግድብ የገንዘብ ማሰባሰብ ዘመቻ በቁጥር አንድ የሀገሪቱ አምባገነን ላይ ደፍራ ጥያቄ በማቅረቧ ነበር፡፡

እ.ኤ.አ መስከረም 2011 አሁን በህይወት የሌለው መለስ በግል ትዕዛዝ በመስጠት ውብሸት እና ርዕዮት “የሽብር ድርጊት ለመፈጸም እና ከአሸባሪ ድርጅት ጋር ተሳትፎ በማድረግ ደባ ለመስራት አሲረዋል” የሚል የፈጠራ የክስ ወንጀል ተፈብርኮ ክስ እንዲመሰረትባቸው አደረገ፡፡

በርዕዮት ላይ የቀረበው “ደባ ለመፈጸም እየተባለ በመለስ ዜናዊ የይስሙላ የዝንጀሮ ፍርድ ቤት ይጠራ የነበረው ማስረጃ በኢሜል የተጻጻፈቸው እና በባለሽቦ ስልክ ስለሰላማዊ ተቃውሞ እና ለውጥ ስለማምጣት በሚል ከሌሎች ጋዜጠኞች ጋር የተነጋገረችው ተቀድቶ የቀረበ ነበር፡፡

ርዕዮት እና ውብሸት ወደ ችሎት ከመቅረባቸው በፊት በነበሩት ሶስት የእስር ወራት ጊዜ ውስጥ የህግ አማካሪ የማግኘት እድሉ አልነበራቸውም፡፡

ሁሉቱም ጋዜጠኞች የህግ አማካሪ እንዳያቀርቡ ተከልክለዋል፡፡

የወያኔ ወሮበላ የዘራፊ ቡድን ስብስብ የይስሙላ የዝንጀሮው ፍርድ ቤት እስር ቤቱ የማሰቃየት ድርጊት እያስፈጸመብን ስለሆነ፣ ከህግ አግባብ ውጭ የሆነ አያያዝ ያለ በመሆኑ እና ህክምና እንዳናገኝ ክልከላ ተደርጎብናልና ምርመራ ይደረግልን በማለት የቀረበውን ውንጀላ አልቀበልም በማለት ውድቅ አደረገ፡፡

ከእስር ቤት እንድትለቀቅ ለመጀመሪያ ጊዜ ጥያቄ በቀረበላት ጊዜ ርዕዮት ከህግ አማካሪዎቿ ጋር መገናኘት እንዳትችል ከተፈረደባት ጊዜ ጀምሮ ለሁለት ዓመታት ያህል ተከልክላ የቆየች መሆኑን አረጋግጣለች፡፡

እ.ኤ.አ ጥቅምት 2012 “የኢትዮጵያ ርዕዮት፡ የጥናካሬዬ ዋጋ“ በሚል ርዕስ ባቀረብኩት ትችት “ክብር በእሳት ፈተና ላይ” በማለት ትክክለኛ ትርጉሙን ግልጽ አድርጌ ነበር፡፡

እ.ኤ.አ የ2012 የደፋር ጋዜጠኝነት ሽልማት/Courage in Journalism Award አሸናፊ መሆኗን ተከትሎ በእጅ ጽሁፏ አዘጋጅታ በዓለም አቀፍ የሴቶች ሜዲያ ፋውዴሽን/International Women’s Media Foundation (IWMF) ስነስርዓት ላይ ቀርቦ እንዲነበብላት በድብቅ ከማጎሪያው እስር በት እንዲወጣ ባደረገችው ደብዳቤ ላይ “ድምጽ ለሌላቸው ድምጽ” ከመሆን የበለጠ ዋጋ የሚያስከፍለኝ ምንም ዓይነት ነገር የለም በማለት ግልጽ አድርጋ ነበር፡፡ ለድፍረቷ ከፍተኛ የሆነ ዋጋ ሊያስከፍላት እንደሚችል እና እውነታውን በጽናት መቀበል እንዳለባት አሳምራ ታውቅ ነበር፡፡

ርዕዮት እ.ኤ.አ ሀምሌ 9/2015 ከመለስ የማጎሪያ እስር ቤት በተለቀቀችበት ዕለት የክርክር አመክንዮዋን እንደገና በድጋሜ አረጋግጣለች፡፡

የፈለገውን ያህል ዋጋ ቢያስከፍልም በኢትዮጵያ ዴሞክራሲ እና ፍትህ እንዲሰፍኑ በጽናት ለመታገል ቆርጣ የተነሳች መሆኗን አውጃለች፡፡ ትክክለኛ የድፍረት ትርጉሙ ምን እንደሆነ ለእኔ እና ለሁሉም ደጋፊዎቿ አስተምራናለች፡፡

የስዊድን ጋዜጠኞች ማርቲን ሽብዬ እና ጆሀን ፔርሰን እራሳቸው አሁን በህይወት በሌለው በመለስ ዜናዊ እ.ኤ.አ ሰኔ 2011 አሸባሪነት በሚል የሸፍጥ ክስ ተመስርቶባቸው ለመጀመሪያ ጊዜ ርዕዮትን በእስርኞች የማማላለሻ አውቶብስ ውስጥ ሆና እጆቿ በካቴና ታስረው ለፌዴራል የመጀመሪያ ፍርድ ቤት በመቅረብ ላይ እንዳለች ያገኟት መሆናቸውን ግልጽ አድርገዋል፡፡

ሽብዬ “ምን እያደረግሽ ነው?” በማለት ጥያቄ አቀረበላት፡፡

ርዕዮት እንዲህ በማለት ምላሽ ሰጠች፣ “እኔ ጋዜጠኛ ነኝ፣ ብቻችንን አይደለንም፣ በርካታ የፖለቲካ እስረኞች ነን እዚህ በአሸባሪነት ወንጀል ተከስሰን ያለነው“ በማለት እስር ቤቶቹን አመላከተችው፡፡

ርዕዮት ለሽብዬ እንዲህ በማለት ነገረችው፣ “በምትፈታበት ጊዜ እኔ ምንም ዓይነት አሸባሪ ያለመሆኔን ለእውነት የምሰራ ጋዜጠኛ መሆኔን ለዓለም ህዝብ ሁሉ ንገርልኝ፡፡“

ሽብዬ ትኩር አድርጎ ተመለከተ እና እንዲህ አለ፣ “እነዚህ ሁሉም ወጣት ኢትዮጵያውያን ጋዜጠኞች ለአንድ ምርጫ ተዳርገዋል፡፡ ብሩህ አዕምሮ ያላቸው እና የተማሩ ናቸው፣ ቀላል የሆነ ህይወትን መምረጥ ይችሉ ነበር፡፡ ሌሎችን የሙያ ዘርፎች መርጠው መሰማራት ይችሉ ነበር፡፡ ሆኖም ግን እውነትን፣ ሀገራቸውን እና ወገኖቻቸውን በማፍቀራቸው ጋዜጠኞች የመሆን ምርጫቸውን ይዘዋል፡፡“

ርዕዮት በፍጹም ብቻዋን አልነበረችም፣

ርዕዮት ዓለሙ፣ እስክንድር ነጋ፣ ውብሸት ታዬ፣ ተመስገን ዳሳለኝ፣ አብርሃ ደስታ፣ የዞን 9 ጦማሪያን እና ሌሎቹ እንደ እነርሱ ተመሳሳይ የሆኑት በኢትዮጵያ የሚገኙት በርካታዎቹ የፖለቲካ እስረኞች ብቻቸውን አይደሉም፡፡ በእያንዳንዷ ዕለት እና ሰከንድ በእዕምሮ እና በመንፈስ ከእነርሱ ጋር ነን፡፡

ርዕዮት ከፍተኛ ተጽዕኖ ማሳደር የሚችሉ ጓደኞች ነበሯት፣

የጋዜጠኞች ተከላካይ ኮሚቴ (ጋተኮ)/CPJ የእርሷ ጉዳይ ከሌሎች በእስር ላይ ከሚገኙት ጋዜጠኞች ጉዳይም ጋር ተመሳሳይ እንደሆነ በማስረጃ የተደገፈ ዘገባ ስላለው ለበርካታ ዓመታት ከፍተኛ የሆነ ጥረት በማድረግ ሲከታተለው ቆይቷል።

ጋተኮ/CPJ በኢትዮጵያ በተደጋጋሚ የሽብር ወንጀል እየተባለ በነጻ ዘገባ ላይ የሚደረገውን የጽሑፍ ምርመራ አውግዟል፡፡

ጋተኮ/CPJ እንዲህ በማለት የኢትዮጵያን መንግስት ለማስተማር እና ወደ ህሊናው እንዲመለስ ሲያስተምር ቆይቷ፣ “የኢትዮጵያ ጨካኝ አምባገነኖች መንግስት አሸባሪ ናቸው ብሎ ከፈረጃቸው ድርጅቶች እና ቡድኖች ጋር ዘጋቢዎች መነጋገር መቻላቸውን አይወድም፡፡ ሆኖም ግን ጋዜጠኞች ማድረግ ያለባቸው እንደ እነዚህ ያሉ ተግባራትን ነው፡፡ ከዚህ ያነሰ ስራን የሚያከናውኑ ከሆነ ዝም ብሎ ተራ ወሬ የሚያስተላልፍ አፈ ቀላጤ የመሆን ትግባራትን መፈጸም ብቻ ነው የሚሆነው፡፡ ባለስልጣኖቹ እንደዚህ ዓይነቶቹን የሞኝ የውንጀላ ክሶች በአስቸኳይ እርግፍ አድርው በመተው ጓደኞቻችንን መልቀቅ አለባቸው፡፡”

ሂዩማን ራይትስ ዎች/HRW በአጠቃላይ ከርዕዮት ጎን ነበር፣

ሂዩማን ራይትስ ዎች/HRW በርዕዮት እና በውብሸት ላይ ተመስርቶ የነበረውን የድድብና ክስ እንዲህ በማለት አውግዟል፡፡ “እንደ ክሱ ፋይል ከሆነ ማስረጃው በዋናነት በድረ ገጽ መስመሮች በመጠቀም በመንግስት ላይ ሸንቋጭ የሆነ ትችቶችን የሚያቀርቡትን እና በስልክ የተደረጉትን ውይይቶች በተለይም በምንም ዓይነት ሁኔታ ከሽብር ወንጀል ጋር ሊገናኙ የማይችሉትን ስለሰላማዊ ተቃውሞ ድርጊቶች የሚደረጉት ውይይቶች ናቸው፡፡ ከዚህም በተጨማሪ በመጀመሪያ በቀረበው የክስ ፋይል ላይ ተከላካዮች ለተከሰሱበት ወንጀል ሌላው ቀርቶ መሰረታዊ የሆኑ የወንጀል ዝርዝሮችን እንኳ ያላሟ ነው…“ በማለት በይፋ ተቃውሞታል፡፡

አምነስቲ ኢነተርናሽናል የተባለው ዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብት ተሟጋች ድርጅትም ከርዕዮት ጎን በመሰለፍ የወያኔ ወሮበላ የዘራፊ ቡድን ስብስብ የይስሙላ የዝንጀሮ ፍርድ ቤት በእርሷ ላይ እያደረገ ባለው የችሎት ሂደት ላይ ያለውን ቁጣ እንዲህ በማለት ገልጿል፡፡ “ምንም ዓይነት የወንጀል ጥፋት ለማጥፋታቸው ሊያስረዳ የሚችል ማስረጃ የለም፡፡ እነዚህ እስረኞች ህጋዊ በሆነ መልኩ መንግስትን በመተቸታቸው ምክንያት እየተቀጡ ያሉ የህሊና እስረኞች ናቸው ብለን እናምናለን፡፡ ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ባስቸኳይ መፈታት አለባቸው፡፡“

ፓምባዙካ የዜና ወኪል/Pambazuka News ርዕዮት መፈታት እንድትችል የውትወታ ዘመቻ አደራጅቶ ነበር፡፡ ፓምባዙካ እንዲህ በማለት አውጆ ነበር፣ “የመንግስትን ኢፍትሀዊነት መርህን መሰረት ባደረገ መልኩ ለእውነት እና ለፍትህ በጽናት በመቆሟ ምክንያት ዓለም አቀፍ ዝናን እንድትጎናጸፍ አስችሏታል፡፡“

ደፋር ጋዜጠኞችን እየመረጠ ሽልማት የሚሰጠው ዓለም አቀፍ የሴቶች ሜዲያ ፋውንዴሽን ሽልማት/International Women’s Media Foundation’s Award የሎስአንጀለስ ታይምስ/Los Angeles Times መጽሔት እ.ኤ.አ በ2012 የአሸናፊነት ሽልማቱን በሰጠበት ወቅት ለርዕዮት እንዲህ በማለት ተሟግቶላት ነበር፣ “ርዕዮት ዓለሙ በቬርሊ ሂልስ በተደረገው ጠቃሚ እራት ግብዣ ላይ ሳትገኝ ቀርታለች፡፡ ሆኖም ግን ጥሩ ይቅርታ ይደረግላታል፡፡ የ31 ዓመቷ ጋዜጠኛ የኢትዮጵያ መናገሻ በሆነችው በአዲስ አበባ ከተማ በሚገኘው እና በጣም አስከፊ በሆነው አይጦች በሚተራመሱበት እና ቃሊቲ እየተባለ በሚጠራው እስር ቤት ውስጥ ታስራ ትገኛለች፡፡ ስለድህነት፣ ስለተቃውሞ ፖለቲካ እና ስለጾታ እኩልነት በድፍረት በመጻፏ ምክንያት ከተበየኑባት አምስት ዓመታት ውስጥ በአሁኑ ጊዜ በሁለተኛው ዓመት እስር ላይ ትገኛለች፡፡“

ርዕዮት ከጎኗ የቆሙ ወንድሞችም አሏት፣

ኤሊያስ ወንድሙ፣ የጸሐይ አሳታሚዎች አሳታሚ፣ በርዕዮት ስም ሽልማቱ ከሚገኝበት ቦታ በመገኘት IWMF ያዘጋጀላትን እና አሸናፊ የሆነችበትን ሽልማት ተቀብሎላታል፡፡

ኤሊያስ በርዕዮት ስም ሽልማቱን ከተቀበለ በኋላ እንዲህ ብሎ ነበር፣ “ርዕዮትን ለዚህ ሽልማት ስጠቁም በእርሷ ላይ ያለውን ድፍረት ለማሳየት ነበር የፈለግሁት፣ ስለሆነም በሀገራችን ያሉ ልጃገረዶች ድምጽ ለሌላቸው ድምጽ የለሾች ድምጽ ለመሆን ከመደፋፈር ወደኋላ አይሉም፡፡ የአንድን መንግስት ፖሊሲ በመጻፍ ትችት የሚያደርግን ሰው በአሸባሪነት መክሰስን እንዴት አድርጎ በመሬት ላይ ማነጻጸር ይቻላል?“

ኤሊያስ እንዲህ የሚል ሌላ አማራጭ ሰጥቶ ነበር፣ “ተገቢ በሆነ ስልጠና እጥረት መሰረት ጋዜጠኞቻችን ፍጹም አይደሉም ሊሆኑም አይችሉም፣ ሆኖም ግን ለዚህ መፍትሄ ሊሆን የሚችለው የሚሰሯቸውን ስህተቶች እየተከታተሉ ወንጀለኛ በማድረግ መቅጣት ተገቢ አይደለም፣ ሆኖም ግን ማረም እና ማስተማር ተገቢ ይሆናል፡፡“

የርዕዮት የእጅ ጽሁፍ ደብዳቤ ከመለስ ዜናዊ የማጎሪያ እስር ቤት ሾልኮ በመውጣት ለIWMF በመድረስ እውነተኛውን የጋዜጠኝነት ድፍረት በተገባር አሳይቷል፡፡ በቁራጭ ወረቀት ላይ በመጠቀም የሚከተሉትን ቃላት አስፍራ ነበር፡

በኢትዮጵያ ወደፊት የተሻለ ነገርን ለማምጣት አንድ ነገር ማበርከት እንዳለብኝ እምነት አለኝ፡፡ በኢትዮጵያ በርካታ ኢፍትሀዊነቶች እና ጭቆናዎቸ ስላሉ በማወጣቸው ጽሁፎቼ አማካይነት ማጋለጥ እና መቃወም አለብኝ፡፡ ምክንያቱም ጋዜጠኝነት እራሴን በፅናት ላሰማራበት የሚገባ ሙያ በመሆኑ ነው፡፡ ለኢህአዴግ ጋዜጠኝነት ማለት ለፕሮፓጋንዳ ስራ ለገዥው ፓርቲ መጠቀሚያ ብቻ አድርጎ እንደሚያየው አውቃለሁ፡፡ ሆኖም ግን ለእኔ ጋዜጠኞች ድምጽ ለሌላቸው ድምጽ የለሾች ድምጽ ናቸው፡፡ ለዚህም ነው የተጨቆኑትን የሚያጋልጡ በርካታ ጽሁፎችን የጻፍኩት፡፡

ነጻነትን ዴሞክራሲን ለመጠየቅ ወደ አደባባይ በመውጣት በመንገዶች ላይ ሰላማዊ ሰልፍ የሚያደርጉ ንጹሀን ዜጎችን በጥይት መደብደብ፣ የተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲ መሪዎችን እና ጋዜጠኞችን ወደ እስር ቤት ማጋዝ…እንዲሁም የመናገር፣ የመደራጀት ነጻነትን መከልከል እና ፕሬስን ማፈን፣ በሙስና መዘፈቅ፣ የአንድ ጎሳ ቡድን በሌሎች ላይ የበላይ ሆኖ መቅረብ የመሳሰሉት ነገሮች የመንግስታችን ጥቂት መጥፎ ስህተቶች ናቸው፡፡ እንደዚህ ያሉ ዘገባዎችን ፈልፍዬ በማውጣት በማሳየው ድፍረት ዋጋ ሊያስከፍለኝ እንደሚችል አስቀድሜ አውቃለሁ፡፡ እናም ያንን ዋጋ ለመቀበል ዝግጁ ነበርኩ፡፡

እ.ኤ.አ በ2013 ርዕዮት የዩኔስኮን የጉሌርሞ ካኖንን ዓለም አቀፍ የፕሬስ ነጻነት ሽልማት/UNESCO Guillemo Cano World Press Freedom Prize አሸናፊ ሆና ተሸልማለች፡፡

ሽልማቱን ከሰጠ በኋላ ዩኔስኮ እንዲህ የሚል ጥቆማ ሰጥቶ ነበር፣ “ወ/ት ርዕዮት ነጻ በሆነ ዓለም አቀፍ የሜዲያ ባለሙያዎች የዳኞች ቡድን ላሳየችው ልዩ የሆነ ድፍረት፣ እምቢተኝነት እና ሀሳብን በነጻ ለመግለጽ ባላት የዓላማ ጽናት ለእርሷ ዕውቅና በመስጠት ለሽልማቱ እንድትቀርብ ተደርጓል፡፡“

ርዕዮት ዓለሙ እ.ኤ.አ ሀምሌ 9/2015 ከአሜሪካ ድምጽ የአማርኛው አገልግሎት ጋር ያደረገችው ቃለመጠይቅ፣

ርዕዮት ዓለሙ በአሜሪካ ደምጽ የአማርኛው አገልግሎት ጋዜጠኛ በሆነው በሰለሞን አባተ ቃለ መጠይቅ ተደርጎላታል፡፡ (ከዚህ በታች ያለው በእንግሊዝኛ ከተረጎምኩት በመውሰድ እንደገና ወደ አማርኛ የተተረጎመ የእራሴ ትርጉም ነው፡፡ የርዕዮትን ቃላት በተቻለ መጠን ትክክለኛ ትርጉማቸውን በማዘጋጀት የቃላት ትርጉማቸውን ብቻ ሳይሆን ተመሳስሎዎችን እና የተለመዱ የቋንቋ አባባሎችንም በማከተት ለማቅረብ ሞክሪያለሁ፡፡)

ወደ እንግሊዝኛ ተተርጉሞ የነበረው ቃለመጠይቅ እንደገና ወደ አማርኛ ተመልሶ ለአንባቢዎች እንደሚከተለው ቀርቧል፡

ሰለሞን፡ ርዕዮት ዓለሙ፣ እንኳን ደስ ያለሽ (ከእስር ቤት በመፈታትሽ ምክንያት) እናም እንኳን በሰላም ወደ ቤትሽ ለመመለስ አበቃሽ፡፡

ርዕዮት፡ እናንተንም እንኳን በሰላም ለማግኘት አበቃኝ፡፡

ሰለሞን፡ ከእስር ቤት በመለቀቅሽ ምክንያት ደስ የተሰኙ በርካታ ሰዎች አሉ፡፡ ለመሆኑ በስንት ሰዓት ነው ከእስር ቤት የተለቀቅሽው?

ርዕዮት፡ ወደ 4 ሰዓት አካባቢ ይሆናል ብዬ አስባለሁ፡፡ ሆኖም ግን ሰዓቱን በእርግጠኝነት አላረጋገጥኩም፡፡

ሰለሞን፡ ጧት ነበር የተፈታሽው?

ርዕዮት፡ አዎ፡፡

ሰለሞን፡ የመፈታትሽ ሁኔታ እንዴት ነበር? ከእስር ቤት ሲለቅቁሽ ምንድን ብለው ነገሩሽ? ከእስር ቤት እንደምትለቀቂ ቀደም ሲል የምታውቂው ነገርስ ነበርን?

ርዕዮት፡ የማውቀው ነገር አልነበረም፡፡ ወደ እኔ በቀጥታ በመምጣት ሂጂ አሉኝ፡፡ ቀልድ ነው የሚል ሀሳብ ነበረኝ፡፡ ለምን እና በምንድን ምክንያት ነው ከእስር ቤት የምለቀቀው በማለት ጥያቄ አቅርቤ ነበር፡፡ እንዲህ አሉ፣ “ከዚህ ውጭ!“ ምክንያቱም ከሌሎች እስረኞች ጋር ምን እንደሚያደርጉ ስለምገነዘብ ነው ለምን እና በምንድን ምክንያት ነው ከእስር ቤት የምለቀቀው በማለት ጥያቄ አቅርቤ የነበረው፡፡ ስለእኔ ከእስር ቤት የመለቀቅ ሁኔታ ያልተጣራ እና የተድበሰበሰ ዘገባ ለህዝብ እናቀርባለን የሚል ሀሳብ ካላችሁ እኔ እውነቱን እንደምናገር ታውቁታላችሁ፡፡ ስለሆነም እውነቱን ለህዝብ ከተናገርኩ በኋላ መልሳችሁ ወደዚህ እስር ቤት የምታመጡኝ ከሆነ ከእስር ቤት አለመቀቄን እወዳለሁ፡፡

ከዚያ በኋላ እንዲህ የሚል ጥያቄ አቀረብኩላቸው፣ “ምንድን ነው እየተካሄደ ያለው?“ እንዲህ አሉ፣ “ይኸው ነው፡፡“ እኔ ይቅርታ ወይም ደግሞ ምንም ዓይነት ቅደመ ሁኔታ አልጠይቅም፡፡ ይቅርታ የመጠየቂያ ጊዜዬ ቀደም ሲል አልፏል እና እርሱንም አልቀበልም በማለት ውድቅ አድርጌዋለሁ ምክንያቱም በመጸጸት ቀርቦልኝ በነበረው ቅጽ ላይ “ወደ ቀድሞው ሁኔታ ተመልሻለሁ የሚል ቋንቋ ነበረበት፡፡” ያጠፋሁት ጥፋት ስላልነበር ያንን ጥፋት ያላጠፋሁ መሆኔን አምኘ ያንን ቅጽ አልሞላም በማለት እንዲመለስ አድርጌ ነበር፡፡

መፈታት የነበረብኝ እ.ኤ.አ ጥቅምት 2014 ነበር፡፡ የእኔ በቅድመ ሁኔታ የመፈታት ሁኔታ አልፏል አሉ፡፡ ስለሆነም ከእስር ቤት እንለቅሻለን፡፡ እንግዲህ የሰጡኝ አጭሩ መልስ ይኸ ነበር፡፡ ለእኔ ከእስር ቤት መለቀቅ መሰረቱ ያ ነበር፡፡

ሰለሞን፡ በነገራችን ላይ የጤንነትሽ ሁኔታ እንዴት ነው?

ርዕዮት፡ ሁላችሁም እንደምታውቁት ከጥቂት ዓመታት በፊት በአንደኛው ጡቴ ላይ የቀዶ ህክምና ተደርጎልኛል፡፡ሌላኛው ጡቴ በአሁኑ ጊዜም እብጠት ይታይበታል፡፡ ቀዶ ህክምና ያስፈልገዋል ብለውኛል፡፡ በእስር ቤት ውስጥ ቀዶ ህክምና እንዲደረግልኝ አልፈለግሁም ምክንያቱም ከዚህ ቀደም በአንደኛው ጡቴ ላይ ቀዶ ህክምና ተደርጎልኛል እናም ጥቂት ወሰብሰብ ያሉ ነገሮች ተፈጥረውብኝ ነበር፡፡ ይህንን ነገር አላደረግሁትም፡፡ በአሁኑ ጊዜ እግዚአብሔር የሚፈቅድ ከሆነ አሰራዋለሁ የሚል ሀሳብ አለኝ፡፡

ሰለሞን፡ የምርመራ ውጤቶች በሁለቱም ጡቶችሽ ላይ ምን ያመላክታሉ?

ርዕዮት፡ ከሁለቱ አንደኛው የተሻለ ነገር ያሳያል፡፡ ሌላኛው ከጊዜ ወደ ጊዜ እያመመኝ ነው የመጣው፡፡

ሰለሞን፡ ከነገርሽኝ ሌላ በተጨማሪ መደበኛ የሆነ የህክምና ምክር እና የትኩረት ድጋፍ አላገኘሽም ነበርን? ጥብቅ የሆነ የሕክምና ክትትል ታደርጊ ነበርን?

ርዕዮት፡ በፍጹም እንደዚያ አልነበረም፡፡

ሰለሞን፡ በየዕለቱ እና በየሳምንቱ የሕክምና ምክር ይሰጥሽ ነበርን? የሕክምና ምክር ወይም ደግሞ የሕክምና ምርመራ ይደረግልሽ ነበርን?

ርዕዮት፡ የለም፡፡ በፍጹም እንደዚያ አልነበረም፡፡ ቀደም ሲል እንዳልኩት ቀዶ ሕክምና መደረጉን ከተውኩት በኋላ እንደ ሳይነስ ለመሳሰሉት ነገሮች ካልሆነ በስተቀር ለዚህኛው ጉዳይ የሕክምና ትኩረት አላገኘሁም ነበር፡፡ የሕክምና ክብካቤ አላገኘሁም፡፡ ምንም ዋጋ የሌለው ነገር ቢሆንም እንኳ የቀዶ ሕክምና እንዳደርግ ነግረውኝ በፍጹም አላደርገውም ብያለሁ፡፡ ምንም ዓይነት የቀዶ ሕክምና ላለማድረግ ወስኘ ነበር፡፡ ምክሮች ያስፈልጋሉ የሚል አስተሳሰብ አልነበረኝም፡፡ ቀደም ሲል እንደተናገርሁት ከወር በፊት የሕክምና ትኩረት አግኝቼ ነበር፡፡ ስለእኔ ጡቶች ጉዳይ ከእነርሱ ጋር ምንም ዓይነት ንግግር አላደረግሁም፡፡

ሰለሞን፡ በእስር ቤት ስለቆየሽበት ሁኔታ ጥቂት ልትነግሪኝ ትችያለሽን? ይቅርታ አድርጊልኝ ወደዚያ መልሸ ልወስድሽ አልፈልግም ነበር፡፡ ሆኖም ግን ስለዚያ ጉዳይ ማወቅ የሚፈልጉ በርካታ አድማጮች ስላሉ ነው፡፡

ርዕዮት፡ አዎ፡፡ ስለዚያ ጉዳይ እንዴት አድርጌ እንደምነግርህ አላውቅም፡፡ እንደ እስረኛው ሁኔታ ይለያያል፡፡ አጠቃላይ በሆነ ለመናገር ስለእስረኞች ያለው አያያዝ ጥሩ ነው የሚባል አይደለም፡፡ ሆኖም ግን የፖለቲካ እስረኞች በተለዬ ሁኔታ ጥሩ በሆነ ሁኔታ የሚያዙ አይደለም፡፡ የእኔን ጉዳይ ብትወስድ ለአንድ ዓመት ከ8 ወራት ያህል ቤተሰቦችን እንዳላይ ተከልክየ ነበር፡፡ እናት እና አባቴን ብቻ እንዳይ ይፈቀድልኝ ነበር፡፡ ባለፉት ሶስት ወራት ብቻ ነው እህቴ መጥታ እንድትጎበኘኝ የተፈቀደው፡፡

ስለሆነም ከቤተሰቦቼ ጉብኝት ጀምሮ መብቶቼ አይጠበቁም ነበር፡፡ ሕጉ የሚለው ነገር ቢኖር የኃይማኖት አባቴን፣ የሕግ አማካሪ ጠበቃዬን እና ሌሎችንም ሰዎች የማግኘት እና እርዳታ እና ምክር የማግኘት መብት እንዳለኝ በግልጽ ተቀምጧል፡፡ ቀደም ሲል እንደተናገርኩት ባለፉት ሁለት እና ሶስት ወራት ብቻ ነበር እህቴ እንኳ መጥታ እንድታየኝ የተፈቀደው፡፡ ለአንድ ዓመት እና ለ8 ወራት ሙሉ እናቴ እና አባቴ ብቻ ናቸው እየመጡ እንዲጎበኙኝ ተፈቅዶላቸው የነበረው፡፡

በእስር ቤት ውስጥ በርካታ ችግሮች ነበሩ፡፡ ለምሳሌ ያህልም የመጽሐፍት ችግር፡፡ መጽሐፍት በተለይም የፖለቲካ መፅሐፍ ለማግኘት እንዲያውም ፖለቲካ የምትል ቃል ያለበት መጽሐፍ በተለይም በአሁኑ ጊዜ ከታዬ እንኳ ከፍተኛ የሆነ ቸግር ነበር፡፡ እንግዲህ መጽሐፍትን ከውጭ ለማግኘት ነው ይኸ ሁሉ ችግር ያለው፡፡ ሌሎችን በርካታ ነገሮችን መግለጽ እችላለሁ፡፡ በአጠቃላይ በእስር ቤት የነበረው ቆይታዬ ጥሩ አልነበረም፡፡ እስር ቤት በፍጹም ጥሩ ነገር ሊሆን አይችልም፡፡ ለእኔ የስቃይ ጊዜ ነበር፡፡

ሰለሞን፡ አባትሽ የአንች የሕግ አማካሪ ጠበቃ ነበሩን?

ርዕዮት፡ አዎ አባቴ የእኔ የሕግ አማካሪ ጠበቃዬ ነበር፡፡ እንደዚሁም ሌላም ጠበቃ ነበረኝ፡፡

ሰለሞን፡ አባትሽን እንደ እራስሽ የሕግ ጠበቃ እንጅ እንደሌላ የሕግ ጠበቃ አልነበረም የምታያቸው?

ርዕዮት፡ አይደለም፡፡ ሁለቱንም በአንድ ጊዜ ማግኘት አልችልም ነበር፡፡ ላለፉት ሁለት ዓመታት ከማንም ጋር ግንኙነት አልነበረኝም፡፡ አባት እና እናቴ ወደ እስር ቤት በመምጣት ይጎበኙኝ ነበር፡፡ ሆኖም ግን አባቴ ለሕግ ምክር አገልግሎት አይመጣም ነበር፡፡ ስለአኔ የህግ ጉዳዮች ምንም ነገር መነጋገር አንችልም ነበር፡፡ ወይም ደግሞ ሌላ የሕግ አማካሪም እንዳገኝ እና ምክር እንድቀበል አይደረግም ነበር፡፡

ሰለሞን፡ በእስር ቤቱ ውስጥ የነበረው ንጽህና ስለምግቡ፣ ውኃው እና ስለሌሎች ተመሳሳይ ነገሮች የነበረው ሁኔታ እንዴት ነበር?

ርዕዮት፡ እኔ በቤተሰቦቼ የሚመጣልኝን ምግብ ነበር የምመገበው፡፡ የእስር ቤቱን ምግብም አይቸዋለሁ፡፡ ጥሩ ብለህ ይመትጠራው ነገር አይደለም፡፡ መጥፎ ነው፡፡ ከፍተኛ ወንጀል ፈጽመዋል ለተባሉ የፖለቲካ አስረኞች የሚቀርበው የተለመደው የኢትዮጵያ እንጀራ እና ወጥ ምግብ በጣም አስቀያሚ ነው፡፡

ሰለሞን፡ የኢትዮጵያ ባለስልጣኖች ስለፖለቲካ እስረኞች ጥያቄ ሲቀርብላቸው የሚሰጡት መልስ “ምንም ዓይነት የፖለቲካ እስረኞ የሉም” የሚል ምላሽ ይሰጣሉ፡፡

ርዕዮት፡ ያ ዓይን ያወጣ ውሸት ነው፡፡ እዚያ በርካታ የፖለቲካ እስረኞች እንዳሉ አውቃለሁ፡፡ ሌላው ቀርቶ ስለ እራሴ ሁኔታ እንኳ ልነግርህ እችላለሁ፡፡ የእኔ ጉዳይ እራሱ በርካታ የፖለቲካ እስረኞች እንዳሉ በቂ ማስረጃ ነው፡፡ እኔን ለእስር የሚያበቃ ምን ወንጀል ሰራሁ? ምናልባትም የእኔን የችሎት ክርክር ሂደት ተከታትለኸው ይሆናል፡፡ ሰለሆነም እነርሱ አሸባሪ የሚል ውንጀላ በመለጠፍ የሀሰት ክስ መስርተውብኝ የችሎት ሂደት ሲካሄድ በነበረው እና ሲቀርብ በነበረው ማስረጃ እንዳያችሁትም ምንም ዓይነት ሽብርተኝነትን ለመፈጸሜ ወይም ደግሞ የሽብር ድርጊት ሙከራ ለመፈጸሙ ሊያቀርቡ የሚችሉት ማስረጃ አልነበራቸውም፡፡

ይልቁንም እውነታው እና ትክክለኛው ነገር በስልጣን ላይ ስላለው ገዥ አካል ትችት በመጻፌ ምክንያት ነበር፡፡ ሆኖም ግን ስለአንዳንድ ነገሮች ትችት በመጻፋቸው ወይም ደግሞ የተቃዋሚ የፖለቲካ ድርጀት አባል በመሆናቸው፣ ወይም ሰዎች ስለመብታቸው በመጠየቃቸው ብቻ የታሰሩ እያሉ ምንም ዓይነት የፖለቲካ እስረኞች የሉም የሚል መልስ መስጠታቸው ይቅርታ አድርግልኝ እና የመካድ አካሄድ ነው፡፡ ሆኖም ያንን የመሰለ ምላሽ በመስጠታቸው በጣም ጥቂት የሆኑ ሰዎችን ብቻ ሊያታልሉ ይችላሉ ብዬ ነው የማምነው፡፡

ሰለሞን፡ አብረውሽ የነበሩት ሌሎች እስረኞች ሁኔታስ ምን ይመስል ነበር? አያያዛቸው፣ መንፈሶቻቸው፣ እንዲሁም ሀሰቦቻቸው ምን ይመስል ነበር? በአጠቃላይ እዚያ በነበርሽበት ጊዜ ያለው የእስር ቤት ሁኔታ ምን ይመስል ነበር?

ርዕዮት፡ ወንጀል ለፈጸመ ሰው እና በእስር ቤት ላለ እንዲሁም ምንም ዓይነት ወንጀል ሳይፈጽም በቁጥጥር ስር ውሎ በእስር ቤት ያለ ሰው ሁሉም እስረኞች ቢሆኑም እንኳ ሰብአዊ መብቶቻቸው ሊጠበቁላቸው ይገባል፡፡ መሆን ያለበት ነገር ይህ ነው፡፡

በአሁኑ ጊዜ ያለው ከምግቡ ሁኔታ ጀምሮ መጥፎ ነገር ነው፡፡ በተለይም በአሁኑ ጊዜ በርካታ እስረኞኝ እየተያዙ እየገቡ እና እስር ቤቱን አጨናንቀውት ባለበት ሁኔታ የሚታየው ነገር ሁሉ አስከፊ ነው፡፡

ባለፉት ሁለት ዓመታት እስር ቤት በቆየሁባቸው ጊዚያት ከአጠቃላይ እስረኛ ህዝብ ተነጥለን ከሌሎች አራት እስረኞች ጋር ነበርኩ፡፡ ሆኖም ግን ሌሎች በጣም በተጨናነቀ ሁኔታ ላይ እየተጠበቁ ያሉበት ሁኔተ ነው የሚታየው፡፡ ስለመድኃኒት፣ ስለህክምና ያለው ሁኔታ በቂ ነው የሚባል አይደለም፡፡

የሕክምና ምርመራ የሚባል ነገር የለም፡፡ የህክምና ምርመራ የምታገኘው በከፍተኛ ሁኔታ በምትታመምበት ጊዜ ብቻ ነው፡፡ ሆኖም ግን ከዚያ ውጭ ለስቃይ ማስታገሻ መድኃኒቶችን ያዝዛሉ፡፡ በአብዛኛው በእስር ቤቱ ያለው ሁኔታ ይህንን ይመስላል፡፡

በሌላ በኩል ደግሞ ከፖለቲካ እስረኞች ጋር ሰላምታ ለማቅረብ የሚሞክር ሰው ካለ በርካታ የሆኑ ችግሮችን እንዲጋፈጥ ይደረጋል፡፡ ቦታው የጭንቀት ቦታ ነው፡፡ ከውጭው ሁኔታ ጋር ሲነጻጸር እንኳ ፍርሀት ንጉስ የሆነበት ግቢ ነው፡፡ በእስር ቤቱ ግቢ ውስጥ የምናየው ነገር እንግዲህ ይህንን ይመስላል፡፡

ሰለሞን፡ በርካታ ችግሮች በምትይበት ጊዜ ምን ዓይነት ችግሮች አሉ? የአካል ስቃይ የማሰቃየት ድርጊቶች ይፈጸማሉን? ድብደባዎች እና ሌሎች ነገሮችም ይፈጸማሉን?

ርዕዮት፡ እኔ እየነገርኩህ ያለሁት ስለሴት እስረኞች ሁኔታ ነው፡፡

ሰለሞን፡ ስለእዚያ ጉዳይ ዘርዘር ባለ ሁኔታ ብትነግሪኝ፡፡ የሴት እስረኞች አጠቃላይ ሁኔታ እና አያያዝ ምን ይመስላል? ከሕግ አግባብ ውጭ የሆነ አያያዝ ፈጸምባቸዋልን?

ርዕዮት፡ አዎ፡፡ይህንን ነው እየነገርኩህ ያለው፡፡ አንድ ሰው የፖለቲካ እስረኛ ጋር ሰላምታ በመለዋወጡ ምክንያት ችግር ሊደርስበት አይገባም ነበር፡፡ ሆኖም ግን ለፖለቲከ እስረኛ ሰላምታ ሲሰጥ ከታዬ ማስጠንቀቂያ ይሰጠዋል፣ ወይም ደግሞ ስለዚያ እስረኛ ጉዳይ የተለየ ትኩረት በመስጠት ይከታተሉታል፡፡ የተለየ ምርመራ ወይም እንደዚህ ያለ ነገር የሚካሄድበት ሆኖ ይቀመጣል፡፡ አየህ ነገሮች በእስር ቤት እንደዚህ ናቸው፡፡

ሰለሞን፡ የወደፊት ዕቅዶችሽ ምንድን ናቸው? በአጭሩ አጠቃላይ ያለሽ ምልከታ ምንድን ነው? ከዚህ በኋላ ምንድን ለማድረግ ታስቢያለሽ?

ርዕዮት፡ ቀደም ሲል እንደተናገርኩት ይህ ድንገተኛ የመፈታት ነገር ነው፡፡ ስለሆነም የነበረህን ጊዜ አጠናቅቀህ ስትወጣ ወይም በድንገት ስለተፈታህበት ነገር ስታውቅ ነው መናገር የምትችለው፡፡ ስለሆነም በድንገት እስከተፈታህ ድረስ ይህ ጥያቄ ለየት ያለ ሊሆን ይችላል፡፡

ሆኖም ግን በአሁኑ ጊዜ የማስበው ነገር ቀደም ሲል ተቋርጦ የነበረውን ህይወቴን እንደገና መምራት መቀጠል ነው፡፡ ለምሳሌ ያህል ምንም ዓይነት ትግል ያካሄድኩ ቢሆንም እንኳ በጽሁፍም ሆነ በማንኛውም በምችለው ነገር ሁሉ ዴሞክራሲ እና ፍትህ የሰፈኑባት ኢትዮጵያ እውን እስከምትሆን ድረስ ሙሉ በሙሉ ትግሌን እቀጥላለሁ፡፡ እንደዚህ የሆነች ኢትዮጵያን እስከማይ ድረስ ትግሌን በተጠናከረ መልኩ እቀጥላለሁ፡፡

(የቃለ መጠይቁ መጨረሻ)፣

ለርዕዮት እና በእስር ቤት ለቀሩት ለሌሎች ወንድሞቿ እና አህቶቿ ያለኝ የእኔ የግሌ አክብሮት፣

ሸክስፒር እንዲህ በማለት ጽፈው ነበር፣ “ጥቂቶች ታላቅ ሆነው ይወለዳሉ፣ ጥቆቶች በሂደት ስኬትን ይጎናጸፋሉ፣ ጥቂቶች ደግሞ በእራሳቸው ላይ በመተማመን ታላቅ ይሆናሉ፡፡“

ለጀግኖች እና ጀግኒቶች በተመሳሳይ መልኩ ማለት ይቻላል ብዬ አስባለሁ፡፡

እንደ ርዕዮት ዓለሙ፣ እስክንድር ነጋ፣ ውብሸት ታዬ፣ ተመስገን ደሳለኝ፣ አብርሃ ደስታ፣ የዞን 9 ጦማሪያን እና ሌሎችም እንደ እነርሱ ያሉ በኢትዮጵያ ውስጥ የሚገኙ የፖለቲካ እስረኛ ዜጎች ጀግኖች እና ጀግኒቶች ሆነው አልተፈጠሩም፡፡ ጀግንነትንም አልፈለጉም ነበር፡፡ እድሉ የሚሰጣቸው ከሆነ ጀግንነትን ብቻውን ይተውታል፡፡ ጀግንነት እና ጀግኒነት ሲባል ብቻቸውን መተው ማለት አይደለም፡፡ ዕድል እና እጣ ፈንታ በጀግንነት ላይ ይተማመናሉ፡፡

በርዕዮት ዓለሙ እና በኢትዮጵያ የመጀመሪያዋ ሴት የፖለቲካ መሪ በነበረችው በብርቱካን ሚደቅሳ መካከል በርካታ በትይዩ የተሰመሩ ልዩነቶችን አስተውላለሁ፡፡ ብርቱካን ተመሳሳይ የሆኑ ከህግ አግባብ ውጭ የሆኑ የእስር ቤት አያያዞች ማለትም ለብቻ ነጥሎ ማሰር እና ማዋረድ ተፈጽመውባታል፡፡ ብርቱካን በፖለቲካው ዘርፍ የመጀመሪያዋ መንገድ ፈጣሪ ብቻ አልነበረችም ሆኖም ግን ለኢትዮጵያ ወጣት ሴቶች ሞዴል እና አርአያ ጭምር የነበረች እንጅ፡፡ በአምባገነኑ የመለስ ዜናዊ የማጎሪያ እስር ቤት በጽናት በመቆም መንፈሰ ጠንካራነቷን በተግባር በማሳየት ትምህርት ሰጥታለች፡፡

ብርቱካን በአሁኑ ጊዜ እርሷ ተሸክማው የነበረውን ዓይነት ኃላፊነት ርዕዮት ተሸክማ ስታይ በኩራት በመሞላት በኢትዮጵያ የሩጫ ቅብብሎሽ ዱላውን ለሌላ በማስተላለፍ በማበረታታት ትመለከታለች፡፡ በእሳት የተፈተነ ክብር ምሳሌ የነበረች መሆኗን ወደ ኋላ መለስ ብላ ስትመለከት ትንሽ ፈገግ ትላለች፡፡

ርዕዮትን እና ብርቱካንን በማሰር ብቸኛ ኃላፊነቱን መውሰድ የሚገባው እና አሁን በህይወት የሌለው አምባገነኑ መለስ ዜናዊን ታሪክ የሰይጣን መልዕክተኛ በመሆኑ ብቻ ሳይሆን የተረገመ እና መቅኖ ያጣ ሰብአዊ ፍጡር ሆኖ ሲታወስ ይኖራል፡፡ ገሀነም በእራሱ እንዳለ ሆኖ መለስ ዜናዊ ሲጨመርበት ግን የገሀነም ገሀነም ይሆናል!

እነዚህ ደፋር ወጣት ጋዜጠኞች እንደ ሌሎች አብዛኞቻችን ሳይሆን የተወሰነላቸውን የዕድል ዕጣ ፈንታ በሚያገኙበት ጊዜ በአካል ጉዳት ስቃይ ወይም በፍርኃት ተሸብበው ወደኋላ አያፈገፍጉም፡፡

እስክንድር ነጋ በራሱ ድረ ገጽ በመጻፉ ብቻ የ18 ዓመታት እስራት ሲበየንበት በመፍራት አንገቱን አልደፋም፡፡

ርዕዮት ዓለሙ የይስሙላው የዝንጀሮ ፍርድ ቤት የ14 ዓመታት እስር ሲበይንባት በሎሌነት መልኩ አላጎበደድችም፡፡

ውብሸት ታዬ ነጻነቱን ለመቀዳጀት የወያኔ ወሮበላ የዘራፊ ቡድን ስብስብን አልለመነም፡፡

ተመስገን ደሳለኝ ለነጻነቱ ሲል ነብሱን አልሸጠም፡፡

አበርሃ ደስታ ደስታ ከሚያምንበት ነገር በመፍራት አላፈገፈገም፡፡

በወያኔ ወሮበላ የዘራፊ ቡድን ስብስብ ከመታሰሩ በፊት እ.ኤ.አ ሀምሌ 9/2014 በራሱ የግንኙነት ድረ ገጽ አብርሃ ደስታ ህወሀት እራሱ ነጻነት ያለው ድርጅት እንዲሆን አጥብቆ ተከራክሯል፡፡ ከህወሀት አባላት ጋር ጠላትነት የማልሆንበት ምክንያት የህወሀትን ካድሬዎች የምሁርነት እጥረት እና ክስረት ስለማውቅ ነው ብሎ ነበር፡፡

ሁሉም የኢትዮጵያ ደፋር ጋዜጠኞች እና የፖለቲካ እስረኞች ሁሉንም ነገር የላይኛው ከንፈራቸው ሳይንቀጠቀጥ ይቀበላሉ፡፡

በምንም ዓይነት መልኩ ለጭቆና አያጎበድዱም፡፡

መሰረታቸውን በመያዝ በጽናት ይቆማሉ፡፡

በፍርኃት እና በባርነት ተቀፍድደው በዘራፊ ወሮበላ አምባገነኖች መዳፍ ስር ነጻነታቸውን ተነፍገው ከሚኖሩ ይልቅ በእስር ቤት ነጻ ሆነው መኖራቸውን መርጠዋል፡፡

ዌንዲ ሸርማን እንዲህ ብለው ነበር፣ “ኢትዮጵያ በመጎልበት ላይ ያለ ዴሞክራሲ የምታካሂድ ሀገር ናት፡፡“ በአባባላቸው ትክክል ናቸው ሆኖም ግን ጊዜው ገና ነው፡፡

ርዕዮት እና የእርሷ ትውልድ የሚገባቸውን ቦታ ሲይዙ ኢትዮጵያ ትክክለኛ በመጎልበት ላይ ያለ ዴሞክራሲን እውን ታደርጋለች፡፡ ርዕዮት ላለፉት አራት ዓመታት ከ17 ቀናት በአምባገነኑ የመለስ ዜናዊ የማጎሪያ እስር ቤት በእስር ስትማቅቅ ባትቆይ ኖሮ ለኢትዮጵያ ዴሞክራሲ ምን ያህል አስተዋጽኦ ታደርግ እንደነበር የሚያስገርም አይሆንም፡፡

ለእስክንድር ነጋ፣ ለውብሸት ታዬ፣ ለተመስገን ደሳለኝ፣ ለአብርሃ ደስታ እና ለሌሎችም በእስር ቤት በመማቀቅ ላይ ለሚገኙት ጋዜጠኞች፣ ጦማሪያን እና የፖለቲካ እስረኞች ታላቅ ክብር አለኝ፡፡

ለኢትዮጵያ የመጀመሪያዋ ጀግኒት እና ለእኔ ኢትዮጵያዊት ጀግና ለርዕዮት ታላቅ ክብር አለኝ!

አምላክ ረዥም እድሜ እንዲያጎናጽፋት እና ትግሏን እንድትቀጥል እመኛለሁ፡፡

“ዴሞክራሲ እና ፍትህ የሰፈኑባት ኢትዮጵያ እውን እስከምትሆን ድረስ ሙሉ በሙሉ ትግሌን እቀጥላለሁ፡፡ እንደዚህ የሆነች ኢትዮጵያን እስከማይ ድረስ ትግሌን በተጠናከረ መልኩ እቀጥላለሁ፡፡” ርዕዮት ዓለሙ፣ እ.ኤ.አ ሀምሌ 9/2015

ኢትዮጵያ በክብር ለዘላለም ትኑር!

ሀምሌ 7 ቀን 2007 ዓ.ም


ጦርነቱ ያስፈራው የሕወሓት አስተዳደር በጎንደር አፈናውን ተያይዞታል

$
0
0

(ጎንደር ፋሲል ግምብ - ፎቶ ፋይል)

(ጎንደር ፋሲል ግምብ – ፎቶ ፋይል)


(ዘ-ሐበሻ) አርበኞች ግንቦት 7 በሰሜኑ የኢትዮጵያ ግዛት በሕወሓት አገዛዝ ወታደሮች ላይ ጥቃት መሰንዘሩን ተከትሎ የሕወሓት መንግስት ደህንነቶች በጎንደር የለውጥ አረአያና አንቀሳቃሽ ይሆናሉ ብለው ያሰቧቸውን ሰዎች እያፈኑ ወዳልታወቀ ስፍራ እየወሰዱ እንደሚገኙ ለዘ-ሐበሻ የመጡ መረጃዎች ጠቆሙ::

በአሁኑ ወቅት በከፍተኛ ፍራቻ ውስጥ የሚገኘው የሕወሓት አስተዳደር በተለይም በጎንደር ከተማ እንዲህ ያለውን የአፈና እርምጃ መውሰድ የጀመረው “አማራው ልቡ ከኛ ከራቀ ቆይቷል; አሁንም ግንቦት 7 እና አርበኞች ግምባርን ደብቆ ያስወርረናል” በሚል ፍራቻ እንደሆነ የደረሰን መረጃ አመልክቷል::

የዘ-ሐበሻ የጎንደር ዘጋቢዎች እንደሚሉት የሕወሓት አስተዳደር በአማራው ላይ ያለው እምነት ከመሟጠጡ የተነሳ አማራውን እስከመናቅና እስከማሸማቀቅ ደርሷል:: በአሁኑ ወቅት በሰሜኑ የኢትዮጵያ ክፍል የተነሳውን ጦርነት ተከትሎ እነዚህ የጎንደር ነዋሪዎች እየታፈኑ የት እንደደረሱ አለመታወቅ በከተማው መነጋገሪያ ሆኗል::

ኃይለማርያም ደሳለኝ የአገሪቱ የባንክ ኢንዱስትሪ ለውጭ ባንኮች ክፍት እንደማይሆን አረጋገጡ

$
0
0

ዛሬ በአዲስ አበባ ታትሞ የወጣው ሪፖርተር ጋዜጣ እንደዘገበው

በሦስተኛው ፋይናንስ ለልማት ጉባዔ በኢትዮጵያ ኢንቨስት ለማድረግ እንዲቻል፣ ‹‹ኢትዮጵያ ራይዚንግ›› በሚባል መጠሪያ በተካሄደ የተጓዳኝ ስብሰባ ላይ፣ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ የአገሪቱ የባንክ ኢንዱስትሪ ለውጭ ባንኮች ክፍት እንደማይሆን አረጋገጡ፡፡
HaileMariam
ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም፣ የባንክ ኢንዱስትሪው ለውጭ ባንኮች ክፍት እንዲደረግ ጥያቄ የቀረበላቸው ከኢስላሚክ ባንክ በኩል ሲሆን፣ ‹‹የአገሪቱን የፋይናንስ ዘርፍ ክፍት በማድረግ የውጭ ባንኮችን የምናስገባበት ጊዜ ላይ አይደለንም፤›› በማለት ምላሽ ሰጥተዋል፡፡ ‹‹አውሮፓውያኑ አሁን የደረሱበት ደረጃ ላይ ደርሰው ነው ባንኮቻቸውን ለውጭ ክፍት ያደረጉት፡፡ እኛ እነሱ የደረሱበት ደረጃ ላይ አልደረስንም፤›› በማለት የባንክ ኢንዱስትሪው አሁን ክፍት ቢደረግ፣ የአገር ውስጥ ባንኮች ባዶአቸውን እንደሚቀሩ፣ ለአገር ውስጥ የንግድና የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ የሚቀርብ ገንዘብ ማግኘት ከባድ እንደሚሆን በመግለጽ ዘርፉ ክፍት አይሆንም ብለዋል፡፡

የውጭ ባንኮች ቢመጡ ለአገር ውስጥ ተበዳሪዎች ምንም ገንዘብ አያቀርቡም ያሉት አቶ ኃይለ ማርያም፣ ‹‹ለአገር ውስጥ አነስተኛና መካከለኛ ተበዳሪዎች ከምታበድሩት ሃምሳ በመቶውን እናቀርባለን ካላችሁ ያን ጊዜ እከፍትላችኋለሁ፤›› ከማለታቸውም በላይ፣ ‹‹በአፍሪካ የባንክ ኢንዲስትሪውን ለውጭ ክፍት አድርጎ የተጠቀመ አገር ካለ ጥሩልኝ፤›› በማለትም ጥያቄያዊ አስተያየታቸውን ሰንዝረዋል፡፡

በመድረኩ ከቀረቡላቸው ሌሎች ጥያቄዎች መካከል በአሜሪካ የሃርለም ኮሚዩኒቲ ከንቲባና የአፍሪካ ስደተኞች የክብር አምባሳደር ‹‹ንግሥቷ እናት›› በሚል የተለምዶ መጠሪያ የሚታወቁት ዶ/ር ዴሊዎስ ብላክሊ ያቀረቧቸው ይጠቀሳሉ፡፡ ንግሥቷ አቶ ኃይለ ማርያምን በመሬት ሽሚያና በተማሩ ሰዎች ፍልሰት ላይ ጠይቀዋቸዋል፡፡ በአፍሪካ የመሬት መቀራመት እንዲቀር፣ ‹‹አፍሪካ አትሸጥም›› በማለት ጠንካራ ንግግር ጋር ጥያቄያቸውን ለጠቅላይ ሚኒስትሩ አቅርበዋል፡፡ ከዚህም ባሻገር በርካታ የተማሩ ሰዎች ወደ አገራቸው በመመለስ ባህላቸውን እየጠበቁ እንዲኖሩ የሚያስችላቸው አሠራር እንዲኖርም ጠቅላይ ሚኒስትሩን ጠይቀዋል፡፡

አቶ ኃይለ ማርያም በበኩላቸው፣ የመሬት ሽያሚያ የሚለው አገላለጽ የተሳሳተ መሆኑንና የምዕራቡ ዓለም ሚዲያዎች የሚያራግቡት ርዕዮተ ዓለም ነው በማለት ተችተዋል፡፡ ‹‹ሰዎችን አናፈናቅልም፡፡ ባዶ መሬት ነው የምናቀርበው፡፡ ባዶ መሬት እንዲሁ መተው የለበትም፣ መልማት አለበት፤›› በማለት ተከራክረዋል፡፡ ከዚህም ባሻገር ‹‹የምዕራባውያን ኩባንያዎች መጥተው ኢንቨስት ሲያደርጉ ማንም አይናገርም፡፡ የቻይናና የህንድ ኢንቨስተሮች ሲመጡ ግን ሁሉም ይቃወማል፤›› ካሉ በኋላ፣ ይህ ፍትሐዊነት የሌለው ርዕዮተ ዓለም መሆኑን ለማስረዳት ሞክረዋል፡፡ ከዚህም ባሻገር የዳያስፖራው ማኅበረሰብ በኢትዮጵያ ኢንቨስት የማድረግ መብት እንዳለው፣ እስካሁንም በአገልግሎት መስክ መልካም የሚባለውን አገልግሎት እየሰጡ ያሉ የአሜሪካ ዳያስፖራ አባላት አገር ውስጥ እንዳሉም ለ‹‹ንግሥቷ›› አስረድተዋል፡፡

በአገሪቱ የኢንቨስትመንት መስህቦች ላይ የኧርነስት ኤንድ ያንግ ማኔጂንግ ፓርነትነር አቶ ዘመዴነህ ንጋቱ፣ እንዲሁም የሶል ሬቤልስ ኩባንያ መሥራችና ማኔጂንግ ዳይሬክተር ቤተልሔም ጥላሁን ንግግር አድርገዋል፡፡ አገሪቱ ለኢንቨስትመንት ያላትን አመቺነትና በአፍሪካ እያደገ የመጣውን የኢኮኖሚ የበላይነቷን በማስመልከት አቶ ዘመዴነህ እንዳስታወቁት፣ ኢትዮጵያ በመጪዎቹ ሦስት ዓመታት ውስጥ በአፍሪካ ሦስተኛዋ ትልቅ ኢኮኖሚ ያላት አገር ለመሆን ተቃርባለች፡፡ በአሁኑ ወቅት ከናይጄሪያ፣ ከደቡብ አፍሪካና ከአንጎላ ቀጥላ በአራተኛ ደረጃ ላይ የምትገኘው ኢትዮጵያ፣ አንጎላን ወደኋላ ልታደርግ ከምትችልባቸው አጋጣሚዎች አንዱ እያደገ የመጣው የውጭ ኢንቨስትመንት ነው ብለዋል፡፡

የዓለም ባንክ ፕሬዚዳንት ጂም ዮንግ ኪም በኢትዮጵያ በርካታ ተስፋ የሚጣልባቸው ሥራዎች መከናወናቸውን ገልጸዋል፡፡ ከአሥራ አምስት ዓመታት በፊት እሳቸውን ጨምሮ ማንም ሰው ኢትዮጵያ የሚሊኒየሙን የልማት ግቦች ለማሳካት ይቻላታል ብሎ ያሰበም የተነበየም እንዳልነበረ ተናግረዋል፡፡

በአርባ ምንጭ ግድግዳ ላይ “ከአርበኞች ግንቦት 7 ጋር ወደፊት”የሚል በመለጠፉ አካባቢው በመከላከያ ሰራዊት ሲታመስ ዋለ

$
0
0

የአርበኞች ግንቦት 7 ህዝብ ግንኙነት ጋዜጣዊ መግለጫ:-

አርበኞች ግንቦት 7 ለአንድነትና ዴሞክራሲ ንቅናቄ በህወሓት አገዛዝ ላይ ተከታታይ ወታደራዊ እርምጃ መውሰድ ከጀመረ ወዲህ የኢትዮጵያ ህዝብ ከመቼውም ጊዜ በላይ ተነቃቅቶ ለለውጥ መነሳሳቱ ታውቋል፡፡ ስልጣኔን አጣለሁ ብሎ ትልቅ ስጋት ላይ የወደቀው የህዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ ዘረኛ ቡድን በበኩሉ ደግሞ ህዝቡን እያፈሰ ወደ ወህኒ ማጋዙን ተያይዞታል፡፡
war
በራሪ ወረቀቶችን ለህዝብ የማሰራጨቱ ተግባር ከሰሜኑ የኢትዮጵያ ክፍል ወደ ደቡቡ የኢትዮጵያ ክፍል መሸጋገር ችሎ በአርባ ምንጭ ከተማ የትግል ጥሪ የያዙ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ወረቀቶች ተበትነዋል፡፡ በተጨማሪም በየምሰሶዎች፣ አጥሮችና የህንፃ ግድግዳዎች ላይ ህዝቡን ለትግል የሚያነሳሱ ፅሁፎች የሰፈረባቸው ወረቀቶች ተለጥፈዋል፡፡
በተለይም ድል ፋና ቀበሌ አስተዳደር ፅ/ቤት በር ላይ “ከአርበኞች ግንቦት 7 ጋር ወደፊት” የሚል ፅሁፍ በጉልህ ሰፍሮ በመለጠፉ አካባቢው በፌደራል ፖሊስ ሰራዊት ተወሮ ከፍተኛ ውጥረት ነግሶ ይገኛል፡፡

በሌላ በኩል ደግሞ ህዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ በጦር ሜዳ እየደረሰበት የሚገኘውን መራራ ሽንፈት ቁጫኝ በህዝቡ ላይ እየተወጣ እንደሚገኝ የአርበኞች ግንቦት 7 ድፅ ሬድዮ ዜና ምንጮች ከተለያዩ የኢትዮጵያ ክፍሎች በመግለፅ ላይ ናቸው፡፡

በተለይም በሰሜን ጎንደር እና በደቡብ ኢትዮጵያዋ አርባ ምንጭ አፈናውና እስሩ በእጅጉ በርትቷል፡፡ ህዝብ በገፍ ወደ ወህኒ እየተጋዘ ይገኛል፡፡

በሰሜን ጎንደር ቋራ ወረዳ ደለጎ “በመንግስት” ሰራተኝነት አገዛዙን የሚያገለግሉ ከ15 በላይ የሚሆኑ ሰዎች ከየቢሯቸው በደህንነት እየተለቀሙ ወዳልታወቀ ቦታ ተወስደዋል፡፡ በአርባ ምንጭም እንዲሁ በርካታ ወጣቶች በደህንነቶችና በህወሓት የታጠቁ ኃይሎች እየታፈኑ በመሰወር ላይ ናቸው፡፡

የአፈናው አና የእስሩ ምክንያት ከአርበኞች ግንቦት 7 ጋር ግንኙነት አላችሁ የሚል ሲሆን በተለይም ከሀምሌ 5 2007 ዓ.ም ጀምሮ በህወሓት ደህንነቶች ቁጥጥር ስር በዋሉት ሀብታሙ ዶልቻ እና ሲሳይ አምባው በተባሉት የአርባ ምንጭ ወጣቶች ላይ ከፍተኛ ሰቆቃ እየተፈፀመ እንደሚገኝ የደረሰን መረጃ ያረጋግጣል፡፡

የዳና ዳራማዋ ተዋናይት በእስራት ተቀጣች

$
0
0

bezawit mesfin
በተለያዩ ፊልሞችና የቴሌቪዥን ድራማዎች ላይ በመተወን የምትታወቀው ተዋናይት ቤዛዊት መስፍን እና ግብረ አበሯ በእስራት መቀጣታቸውን አፍቃሬ ሕወሓት የሆነው ራድዮ ፋና ዘገበ::

በአዲስ አበባ ከተማ በኮልፌ ቀራንዮ ነዋሪ የሆኑት ተከሳሾቹ በእስራት የተቀጡት ከታዘዘላቸው ውጭ ተጨማሪ ገንዘብ ከባንክ ቤት በማውጣት ለግል ጥቅማቸው በማዋላቸው ነው።

የ22 አመቷ ተዋናይት ከግብረ አበሯ ጋር በመሆን በተሰጣቸው የ4 ሺህ ብር ቼክ ላይ ከፊት ለፊቱ ሁለት ቁጥርን በመጨመር ያልተፈቀደላቸውን 24 ሺህ ብር ከወጋገን ባንክ ሰባራ ባቡር ቅርንጫፍ አውጥተዋል።

ተከሳሾቹ ለአቶ ዮናታን ባልቻ መኪና በማከራየት የኪራይ ስምምነት ውል ያላቸው ሲሆን፥ በውላቸው መሰረትም ሚያዚያ 8 ቀን 2005 ዓ.ም ከምሽቱ 2 ሰአት አካባቢ የ4 ሺህ ብር ቼክ ተቀብለዋል።

ግለሰቦቹ ሚያዚያ 12 ቀን 2005 ዓ.ም ላይም ከመኪና ተከራዩ አቶ ዮናታን በተቀበሉት የ4 ሺህ ብር ቼክ ላይ ከፊት ለፊቱ 2 ቁጥርን በመጨመር ተጨማሪ 20 ሺህ ብር ከባንክ ቤቱ አውጥተዋል።

በዚህም መሰረት የፌደራሉ አቃቤ ህግ ተከሳሾቹ የማይገባቸውን ብልጽግና ለማግኘት በማሰብ በፈፀሙት ወንጀል ክስ በመመስረት የሰውና የሰነድ ማስረጃዎችን አቅርቧል።

የፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት 5ኛ የወንጀል ችሎትም ተከሳሾቹ የወንጀል ድርጊቱን ማስተባበል ባለመቻላቸው ጥፋተኛ ብሏቸዋል ።

ተከሳሾቹ ወንጀሉን በስምምነት በማበር የፈፀሙት በመሆኑ ቅጣቱ ከፍ ብሎ እንዲወሰን አቃቤ ህግ የቅጣት ማክበጃ አቅርቧል።

ፍርድ ቤቱም የግራ ቀኙን ክርክር ካዳመጠ በኋላ ተከሳሾቹ ያላቸውን የቅጣት ማቅለያ እንዲያቀርቡ ጠይቋል።

በዚህም 1ኛ ተከሳሽ ቤዛዊት መስፍን የዕድሜዋን ወጣትነት፣ ከዚህ ቀደም በምንም አይነት የወንጀል ድርጊት አለመሳተፏንና የቤተሰብ አስተዳዳሪ መሆኗን በቅጣት ማቅለያነት አቅርባለች።

2ኛ ተከሳሽ አቶ ነቢል ይማም ምንም አይነት የቅጣት ማቅለያዎችን አላቀረበም።

የፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት 5ኛ የወንጀል ችሎትም 1ኛ ተከሳሽን በ6 ወር ቀላል እስራትና በ1 ሺህ 500 ብር እንዲሁም 2ኛ ተከሳሽን በ1 አመት ከ6 ወር እስራት እና በ3 ሺህ ብር እንዲቀጡ ወስኗል።

አንቀፅ 39: የራስን ዕድል በራስ መወሰን ሲባል –አስራት አብርሃም

$
0
0

 

Asrat Abrha

አስራት አብርሃም

ውብሸት ሙላት በተባለ የህግ ምሁር ሰሙኑ ገበያ ላይ የዋለው “አንቀፅ 39 የራስን ዕድል በራስ መወሰን” የተሰኘ መፅሐፍ መግቢያ (ፀሐፊው የቃላት ክልሼነት ለማስወገድ ነው መሰል ማስረጊያ የሚል ርዕስ ሰጥቶታል) “የራስን ዕድል በራስ የመወሰን መብት አዲስ አይደለም፤ አሮጌ ነው። ብዙ ተፅፎበታል።” በማለት ነው የሚጀምረው፤ በርዕሰ ጉዳዩ ላይ በተቃውሞም፣ በድጋፍም ጭምር በልዩ ልዩ ሚዲያዎችና መንገዶች ሲፃፍበት እንደነበር ይገልፅና ይህን መፅሐፍ ማዘጋጀት ያስፈለገበት ምክንያት ሲገልፅ ደግሞ “ለአብዛኛው ሰው በሚሆን መልኩ ጠቅለል ብሎና ራሱን ችሎ በመፅሐፍ መልኩ ስለሌለ ይህንን ክፍተት ለመሙላት በማሰብ” መሆኑን ይገልፃል።

ይህ መፅሐፍ በኢፌዲሪ ህገመንግስት አንቀፅ 39 ዘጠኝ ላይ ያለው የራስ ዕድል በራስ የመወሰን እስከ መገንጠል የሚለውን ሀሳብ ከታሪክ፣ ከፍልስፍና፣ ከህግና ከፖለቲካ አንጻር እያነሳ በጥልቀት የሚተነትን ነው፤ እኔም ሌሎች የሀገራችን ምሁራን በስፋትና በጥልቀት እስኪተነትኑትና እስኪፈትሹት ድረስ እንደመጥምቁ ዮሃንስ መንገድ ልጠርግ በማሰብ ነው በዚህ መፅሐፍ ዙሪያ አንድ ሁለት ለማለት የወደድኩት።

የመፅሐፉ የመጀመሪያው ምዕራፍ ንዑስ ርዕስ “የብሄር ጥያቄ” የሚል ሲሆን ፀሐፊው በኢትዮጵያ ጨቋኝ ከሚባለው ብሄር የተገኘው ነው ያለውን ዋልሊኝ መኮንን “ኢትዮጵያ የአንድ ብሄር ሀገር ሳትሆን የብዙ ብሄረሰቦች ሀገር ናት” ገፅ (3-4) በማለት ድፍሮ ለመጀመሪያ ጊዜ መፃፉን ይነግረናል። የአንድ የሶፊስቶች ተረት በማምጣት፤ የብሄር ጥያቄ የብሄር ጭቆና ውልድ መሆኑን ይገልፅና የጭቆናው ዓይነትና ደረጃው ግን ያን ያህል እንደሚባለው የተጋነነ እንዳልሆነ ነው የሚያትተው፤ ተረቱ የሚለው እንደዚህ ነው፤ አንድ ሰው በደል ይደርስበትና ክስ ለማቅረብ ወደ ፍርድ ቤት ይሄድና ለፍርድ ቤቱ የሚያስገባውን ማመልከቻ ለአንድ ራቦር ፀሐፊ እየነገረ አፃፈ አሉ፤ ፅፎ እንደጨረሰ ለባለጉዳዩ ያነብለታል፤ ሲነበብለት ባለጉዳዩ  ስቅስቅ ብሎ ማልቀስ ይጀምራል፤ የፃፈለት ሰውዬ “ምነው ጌታዬ ማልቀስዎ?” ብሎ ቢጠይቀው “ለካስ ይህን ያክል ተበድዬ ኑሯል? አለ ይባላል” (ገፅ 5) ይልና ፀሐፊው ሲቀጥል በእርግጥ “ሰውዬው ተበድሏል፤ ትንሽ የበደል ጫፍ ያገኘው ራቦር ፀሐፊ እጅግ አጋንኖና አጣፍጦ እንደፃፈው ሁሉ የኢትዮጵያ ውስጥ የተከሰተውን ከራቦር ፀሀፊው አድራጎት ጋር ሲያመሳስሉት ይሰማል” ይለናል። ዋልሊኝ ሲል ሰምተው “ለካ ይህን ያህል ተበድለን ኖረናል” ብለው የብሄር ጥያቄ እንዳጎኑት ዓይነት አድርጎ ነው የሳለው የሚመስለኝ፤ ለማንኛውም ዋልሊኝ መኮንን ደፍሮ ፃፈው እንጂ በያኔዋ ኢትዮጵያ የብሄር ጥያቄና ጭቆናው ጣሪያ የነካ ጉዳይ የነበረ ለመሆኑ ምንም ጥርጥር የለውም፤ ጥያቄው ራሱ አሁን ያፈራው ውጤት በማየትም መረዳት የሚቻል ነገር ነው።

በዚህ የብሄር ጥያቄ ላይ በህግ መንግስቱ የሚታየው ጉድለት አንድ ብሄር ወይም ብሄሮች ስለሚለያዩበት እንጂ አንድ ለመሆን ወይም ለመጠቃለል ቢፈልጉ ስለዚህ ጉዳይ ምንም ያለማለቱን ልብ ብሎታል፤ ስለዚህ ጉዳይ ሲገልፅ “የእኛ ህገ መንግስት ፈፅሞ የብሄሮችን መዋሃድ ወይንም ወደ አንድ ብሄር የመጠቃለል አዝማሚያን በቃልም በተግባርም አላማው አላደረገም፤ ተቃራኒው የበለጠ እውነት ይመስላል” (ገፅ 9-10) ይላል፤ ይሄ ተገቢ የሆነ ምልከታ ነው። ህገ መንግስቱ ከኢትዮጵያ መገንጠል እንደፈቀደ ሁሉ ወደ ኢትዮጵያ መጠቃለል የሚፈልጉ ህዝቦች ወይም አንድ ብሄር ከሌላ ብሄር ጋር መዋሃድና መጠቃለል ቢፈልግ ስለሚቻልበት ሁኔታ አለማስቀመጡ የህገ መንግስቱ መሰረታዊ ዓላማ ምን እንደሆነ ግርታን ነው የሚፈጥረው፤ ህገ መንግስቱ ሲረቀቅ እንደዚያ ቢደረግ ኖሮ  አንቀፁ ፍትሃዊነት የሚንፀባረቅበት በሆነ ነበር።

ፀሀፊው በስልሳዎቹ ነበረው ዓለም አቀፍና ሃገራዊ የብሄርተኝነት ትግል እንቅስቀሴ ከዳሰሰ በኋላ በእኛ ሀገርም በዚያ ዘመን የነበሩ ልሂቃን ጥያቄው በማራገብና በማጦዝ እንዚህ ደረጃ ላይ እንዳደረሱት ነው የሚያትተው፤ “የዚያን ዘመን ልሂቃን የብሄርን ጉዳይ በየአገኙት አጋጣሚ እና መድረክ ሰብከዋል። የብሄር ብሄረሰብም ስልጣን ትምጣ ብለው ተመኝተዋል። ከዚያም እነዚህ ልሂቃን ህዝቡ ከማለት ፈንታ ሕዝቤ በማለት ሲጠሩ ተስተውለዋል ከዚያም ያን ህዝብ (የብሀረሰብ አባል) ያኔ የሚለውን ልሂቅ እንደሚከተል ቀድመው ያውቁታልና!

እስቲ ላሙን ንዳው አቧራው ይነሳ

ይከተል የለም ወይ ኮርማው እያገሳ

እንደሚባለው መሆኑ ነው፤ ብሄርተኝነት ስትጎንና ስለብሄር ሲወራ የብሄሩ አባል እያገሳ መከተሉ አይቀሬ ነው” በማለት ነው የሚያስቀምጠው።

የዚህ የብሄር ጥያቄ ጉዳይ አላግባብ ሲለጠጥና ሲራገብ የሚኖረው አደገኝነት ሲብራራ ደግሞ አደጋው እንደ ዩጎዝላቪያና እንደ ሩዋንዳ ለጭፍጨፋና ለዘር ማጥፋት ወንጀል ምክንያት እንደሚሆን ነው የሚያትተው። ለዚህ አደገኛ አካሄድ በእኛ ሀገር አልፎ አልፎ የሚታየው ዘርን መሰረት ያደረገ የህዝቦች መፈናቀልና ግጭት እንደማሳያ መቅረብ የሚችል ነው።

በኢትዮጵያ በዘመነ ኢህአዴግ የብሄር ጥያቄ አፈታት በተመለከተ ፀሀፊው ሲያስረዳ ስልጤ፣ መንጃ እና ቅማንት የተባሉ ብሄረሰቦች ጉዳይ ያነሳና በእነዚህ ብሄሮች ጥያቄ ላይ የተጠሰው ምላሽ የሚታየው ተቃርኖና መፋለስ ያስቀምጣል። በሌላ በእኩል ደግሞ በፌደራሉ መንግስታዊ መዋቅር ውስጥ የሚታየው ፍፅም ያልተመጣጠነ ስልጣን በማንሳት በገዥው ፓርቲ የሚሰበከው የብሄር ብሄረሰቦች እኩልነት እውነትነት የሌለው ፕሮፖጋናንዳ መሆኑን በምሳሌ ነው ያስቀመጠው፤ ቁልፍ የሚባሉ መንግስታዊ የስልጣን እርከኖች በእነማን እንደተያዙ በማሳየት።እንደዚሁም በደሬዳዋ አስተዳደርና የሃረሪ ክልል አፈጣጠርን በማምጣት ኢህአዴግ መራሹ መንግስት የብሄር ጥያቄዎችን ለመፍታት የሄደበት መንገድ ከራሱ ከህገ መንግስቱ ሳይቀር ምን ያህል እንደሚቀረን ያሳየናል።

በምዕራፍ ሰባት ላይ ደግሞ የአማራ ጉዳይ ነው የሚያነሳው። አማራ የሚባል ብሄር አለ ወይስ የለም የሚለው የምሁራኑ ክርክር ያነሳና የለም የሚሉትን ትንሽ ጎሸም ያደረጋቸው ይመስለኛል። ይህ ምዕራፍ የሚጀምረው

… እና አማራ ነኝ … መከራ የመከረኝ

መስዋዕትነት ያጠነከረኝ … ፍቅር የተዘከረኝ…

ብፈራንኳ ፍቅርን ነው’ንጂ … በሌላ አልጠረጠርም

ማንም እንዳሻው ለክቶ … እንዳሻው ሊቆርጠኝ ቢያልም…

ከልክ አልፌ አላጥርም

ጉራም ቢሆን ልቀናጣ …

ስሞ ባያሳድገኝ … ነክሶ እሚያነቃኝ አላጣ …

በሚለው የሙሉጌታ ተስፋዬ ግጥም ነው የሚጀምረው። ከዚህ ግጥም ወረድ ብሎ እንዲህ ይለናል “ስለአማራ መፃፌ፣ አማራ ብሄር ስላልሆነ ወይንም የማንነት ጥያቄ ስላነሳ ሳይሆን አንዳንድ ምሁራን ስለአማራ ጉዳይ ሲፅፉ አማራ የሚባል ብሄር የለም በማለት የብሄርነት ህልውናውን ጭምር ከመጠራጠራቸው የተነሳ ነው። … እንደውም አማራነትን ከኢትዮጵያዊነት እና አልፎ አልፎም ከክርስቲያንነት ጋር አምሳያ በማድረግ ሲያትቱ ይስተዋላል።”

ውብሸት ይህን ዓይነት ዝንባሌ መኖሩን ካወሳ በኋላ ለማጠናከርያነት የፕሮፌሰር መስፍን መከራከሪያ ያነሳል፤ “እሳቸው (ፕሮፌሰር መስፍን) ሊቃውንት አማራ የሚለው ቃል ከስርወ ቃሉ በመነሳት ነፃ፣ የተመረጠ፣ መገዛትን የማይወድ ወዘተ ሕዝብ ነው በማለት የሰጡትን ትርጓሜ መነሻ ያደርጋሉ። አማራ ማለት ነፃ ሕዝብ ማለት ነው ከሚለው አንፃር ብዙም ፍንጭ የማይገኝ ቢሆንም ነፃነትን የሚወድ ለማለት ነው ከተባለም  ነፃነትን የሚጠላ ህዝብ ያለ ስለማይመስለኝ ይህ ዓይነቱ አተረጓጎም ብዙም ስለብሄሩ የሚገልፀው ነገር ያለ አይመስልም”  በማለት ነው የፕሮፌሰር መስፍን  ሀሳብ በምክንያት ውድቅ የሚያደርገው። ገፅ 73 ላይ ደግሞ “ፕሮፌሰር መስፍን ቀጥለውም የተለያዩ ሰዎች “አማራ ነኝ” ሲሉ ክርስቲያን ነኝ ማለታቸውንም እንደሆነ በመግለፅ ክርስቲያን ከሚለው ጋርም ያመሳስሉታል” በማለት አስቀምጦታል፤ በመጨረሻ ይህን ሀሳብ ሲያጠቃልለው “ሊቃውንት ከስርወ ቃሉ በመነሳት ትርጉም የሰጡት አማራ የሚባል ቢያንስ ህዝብ በመኖሩ ነው። የአለቃ ታዬም የአማራን ህዝብ ከየት መጣነት አስረዱ ከማለት ውጪ የለም አላሉም።” በማለት ነው መከራከሪያውን የሚዘጋው። እንግዲህ እኔ የለሁበትም፤ ፕሮፌሰር መስፍን  በህይወት ስላሉ መልስ ይስጡበት። አማራ የለም የሚለው መከራከሪያ የአንድ ህዝብ ህልውና መካድ ብቻ ሳይሆን እንግዲህ ይሄ ጨቋኝ የማሳጣት ሴራ ወይም ወንጀል ተብሎ ያለማስከሰሱም አንድ ነገር ነው።

ይልቅ አንድ ነገር ትዝ አለኝ፤ መንጌ ብሶት የወለዳቸው የኢህአዴግ ልጆች ሱሉልታ በደረሱ ጊዜ ዕቃውን ሁሉ ወደ ዝምባዌ ከሸካከፈ በኋላ በቴሌብዥን ቀርቦ በቅጡ የማያውቀውን የኢትዮጵያ ታሪክ ሲደሰኩር የዋለ ዕለት “አማራ ማለት በተራራ ላይ የሚኖር ነፃ ህዝብ ነው፤ ትግሬውም በተራራ ላይ ይኖራል፤ ሌላውም እንደዚሁ በተራራ ላይ ይኖራል እንግዲህ ማነው አማራ?!” ብሎ ነበር ያለው፤ ለካ እንደ ሁለተኛ ክፍል ተማሪ ከፕሮፍ ሸምድዶ ኖሯል፤ በአግባቡ ለመሸምደድም እኮ ልምድና እርጋታ ይጠይቃል፤ ከሄደ በኋላ እንደተሳሳተ ገብቶት ነው መሰል ከቀይ ሽብሩ ለምን ተውኳቸው የሚል ዓይነት የፀፀት ምልክት አሳይተዋል ለገነት አየለ በሰጣት ቃለመጠይቅ ላይ!!

በዚህ መፅሐፍ ላይ ስፊ ትኩረት የተሰጠው ሌላው ጉዳይ የመገንጠል ጉዳይ ነው፤ ይህ አንቀፅ በህገ መንግስቱ እንዲካተት ሆኖ በፀደቀበት እለት የነበሩ ስሜቶች ለማሳየት በወቅቱ እዚያ የነበሩት እና አሁን ሁለቱም በህይወት የሌሉት ነገር ግን ፍፅም ተቃራኒ አቋም የነበራቸው ሻለቃ አድማሴ ዘለቀ እና ዶ/ር አብዱልመጅድ ሁሴን የተናገሩትን አስቀምጠዋል፤ ሻለቃ አድማሴ “በትናንትናው ዕለት (ህዳር 13/1987 ዓም) ጥቁር ክራቫት አድርጌ ነው የዋልኩት። 90% የሚሆነው የኢትዮጵያ ሕዝብም በትናንትናው ዕለት በማዘን ወደ እግዚአብሄር ፀልዮአል፤ በኢትዮጵያ ታሪክ ከዚህ የከፋ ውሳኔ ተወስኖ፣ ከዚህ የከፋ ህገ መንግስት ወጥቶ አያቅም፤ ጥቁር ቀን ብሎ አውግዞታል” በማለት የአንቀፁን መፅደቅ ሲኮንኑት፤ በተቃራኒው ደግሞ ዶ/ር አብዱልመጅድ “99.9% የሚሆነው የኢትዮጵያ ሕዝብ የደስታ ቀን ነው። አንቀፅ 39 ትናንት ባይፀድቅ ኖሮ ግን ለብዙዎች ክፉ ቀን ይባል ነበር፤ ትናንት የፀሀይ ቀን ነው” በማለት ነበር ደስታቸውን የገለፁት።

ፀሀፊው የራስ ዕድል በራስ መወሰን እስከ መገንጠል የሚኖረው ጥቅም እና ጉዳት ሚዛናዊ በሆነ መንገድ በምሁራዊ ትንተና አስደግፎ አቅርቦታል፤ ከአሁን በፊት ከነበረው የእርግማንና የውግዘት አቀራረብ በተለየ ሁኔታ በምሁራዊነት ተጠያቃዊ መንገድ ትርፍ እና ኪሰራው ጉዳትና ጥቅሙ ለማሳየት ጥረት ማድረጉ ነው አንዱ የዚህ መፅሐፍ ጥቅሙ! ይህን መፅሐፍ አንብበን ስንጨርስ በቂ የሆነ እውቀት ስለመገጠል እንደኖረን ያደርገናል፤ መገንጠል ለሚፈልጉ ኃይሎችም ሆነ መገንጠል ለሚቃወሙ ኃይሎች ለሁለቱም እኩል ጠቃሚ የሚሆን ነው፤ ሁለቱም ወገኖች ቆም ብለው እንዲያስቡ የሚያደርግ ነው። በሌላ አቅጣጫ ካየነው ደግሞ ጥቅሙናን ጉዳቱን በትክክል ሳይገነዘቡ አንድን ነገር መቋወምም ሆነ መደገፍ ተገቢም አዋጭም ስለማይሆን ነው።

ሌላው በዚህ መፅሐፍ የምናገኘው አዲስ እውቀት የራስን እድል በራስ መወስን እስከመገንጠል መብት በህግ መንግስት ደረጃ ያስቀመጠች ሀገር ኢትዮጵያ ብቻ ያለመሆኗ ነው። ከዚህ በፊት ሶቬየት ህብረት እና ዩጎዝላቢያ በህገ መንግስታቸው ላይ የራስን እድል በራስ መወስን እስከመገንጠል መብት አስቀምጠው እንደነበር ይታወቃል፤ ነገር ግን ሀገራቱ ከሶሻሊዝም መውደቅ ጋር ተያይዞ ሲፈራርሱ ይሄ አንቀፅ እንዲቀር ተደርጓል። በጣም አዲስ የሚሆነው እስካሁን ስሟን በቅቱ ሰምተናት የማናውቅ ሴንት ኪትስ እና ኔቪስ የምትባል የሁለት ደሴት ጥምር ሃገርም እንደዚሁ አንዷ ደሴት መገንጠል ከፈለገች ያለምንም ቅድመ ሁኔታ መገንጠል እንደምትችል በህግ መንግስቷ ላይ ማስቀመጧን አስፍሯል። የሚገርመው ደግሞ የአንዷ ደሴት ገዥው ፓርቲና ተቋሚው ፓርቲ ለሴቷን ለመገንጠል በደሴቷ ፓርላማ ላይ ተስማምተው የነበረ ቢሆንም ህዝቡ በተሰጠው ሪፈረንደም ግን በአንድነት ለመኖር ፍላጎት በማሳየቱ የመገንጠሉ ጉዳይ በዚያው ቀርቷል፤ በሌላ ሁኔታ ደግሞ በህገ መንግስታቸው ላይ የመገንጠልን መብት ማያሰፍሩም፤ አንድ ህዝብ ወይም አከባቢ የመገንጠል ሀሳብ ካነሳ እንደ አንድ ዴሞክራሲያዊ ጥያቄ ተወስዶ ሪፈረንደም የሚሰጥበት ሁኔታ እንዳለ ከልምድ ወይም ከታሪክ የምናየው ነገር ነው። ኖርዋይ ከስዊዲን የተገነጠለችው በዚሁ ሁኔታ ነው፤ ሌሎችም አሉ። የካናዳዋ ኩቤክ ግዛትና የታላቋ ብሪቴን እስኮትላድ ሪፈረንደምም ማየት ይቻላል፤ በእነዚህ ሁለት ግዛቶች ህዝቡ እንዲገነጠል ወይም አብሮ እንዲኖር ሪፈረንደም ተስጥቶት በሁለቱም ቦታዎች ህዝቡ አብሮ መኖሩ መርጦ መገንለጠሉን ውድቅ አድርጎታል።

ነገር ግን ገለልተኛ የሆኑ መንግስታዊ ተቋማት በሌሉበት፤ ህዝቡም በነፃነት መወሰን በማይችልበት እንደኛው ዓይነት ሀገር ለአንድ ህዝብ ሪፈረንደም ቢሰጥ የፖለቲካ ልሂቃኑ የሚፈልጉት ነገር ይፈፀማል እንጂ የህዝቡን ይሁንታ በትክክል ለማወቅ አስቸጋሪ ነው የሚሆነው። ውብሸት ስለዚህ ጉዳይ ሲያትት “አምባገነኖች ፈላጭ ቆራጮችም ሕዝበ ውሳኔን እንዲከናወን ያደርጋሉ። ሕዝበ ውሳኔን አይፈሩትም፤ ይልቁንም ይደፍሩታል። ህዝብን መድፈር የተለማመደ ህዝብን እንዳሻው በማድረግ የሚገዛ መሪ የሕዝበ ውሳኔን ውጤት ምን ማድረግ እንዳለበትና ምን እንደሚሆን ቀድሞ ይወስንና ሕዝቡ ድምፅ እንዲሰጥ ያደርጋል። የህዝብ ድምፅ የፈጣሪ ድምፅ ነው የሚለውን አባባል ቀይረው የቄሳሩ ድምፅ የህዝቡ ድምፅ ነው ይሉታል። የፕሬዝደንቱ ወይንም የጠቅላይ ሚኒስትሩ ወይንም የገዥው ፓርቲ ውሳኔ የህዝቡ ውሳኔ ይሆናል።”

የሆኖ ሆኖ ከዚሁ የመገንጠል ሀሳብ ጋር መኖራችን ካልቀረ ስለምንነቱ፣ ስለአተገባበሩና ስለአጠቃላይ ባህርይ በደንብ አውቆ መቆየቱ ጠቃሚ ነው የሚመስለኝ፤ ለመገንጠልም መገንጠል ለማስቀየትም ስለጉዳዩ በቂ እውቀት ይዞ መገኘት አስፈላጊ ነው።ለዚህ ደግሞ ይሄ የውብሸት መፅሐፍ ጠቃሚ ሆኖ አገኝቸዋለሁ።

Viewing all 15006 articles
Browse latest View live