Quantcast
Channel: Ethiopian News | ዘ-ሐበሻ | Latest News Provider | News For All
Viewing all 15006 articles
Browse latest View live

ሰበር ዜና –የአንድነት ፓርቲ አመራሮች ቤት በፖሊሶች እየተበረበረ ነው

0
0

ብርበራው ቀኑን ሙሉ እንደሚደረግ ታውቋል
===============================
UDJበደቡብ ወሎ ዞን በሀይቅ ከተማ የሚገኙ የአንድነት ፓርቲ አመራሮችና አባላት ቤት ላይ ዛሬ ከማለዳው 12 ሰዓት ጀምሮ ብርበራ እንደተጀመረ የዞኑ የአንድነት ፓርቲ አመራሮች ለፍኖተ ነፃነት አስታወቁ፡፡
የአንድነት ፓርቲ የወረባቡ ወረዳ ሰብሳቢ አቶ እድሪስ ሰኢድ ለፍኖተ ነፃነት እንዳስታወቁት ዛሬ ከማለዳው 12 ሰዓት ጀምሮ “የጦር መሳሪያ ሰውራችኋል” በሚል ፖሊሶችና ሚኒሻዎች በሀይቅ ከተማ ባሉ ከ16 በላይ በሚሆኑ የአንድነት ፓርቲ አመራሮችና አባላት መኖሪያ ቤት ውስጥ ብርበራ አካሂደዋል፡፡ ብርበራው ከተካሄደባቸው አመራሮች መሀከል አንዱ የሆኑት የወረዳው የአንድነት ፓርቲ የፋይናንስ ኃላፊ አቶ አራጌ ሑሴን ለሪፖርተራችን እንደገለፁት 5 ፖሊሶችና 1 ሚሊሻ ከማለዳው 12 ሰዓት ጀምረው መኖሪያ ቤታቸውን ፈትሸዋል፡፡ አቶ አራጌ ሁሴን አክለውም “እኔ ሰላማዊ ሰው ነኝ ምንም አታገኙም አልኳቸው፤እንዳልኩትም 2 ሰዓት የፈጀ ብርበራ አድርገውም አንዳች ሳያገኙ ወጥተዋል” በማለት ገልፀዋል፡፡
“ብርበራው መንግስት በአንድነት አባላት ቤት ውስጥ የጦር መሳሪያ አገኘሁ በሚል የተለመደ ድራማ ለመስራት እንደተዘጋጀ የሚያስረዳ ነው” ያሉት የአንድነት ፓርቲ የደቡብ ወሎ ዞን ሰብሳቢ አቶ ብስራት አቢ ኢህአዴግ የደቡብ ወሎ ህዝብ በግዳጅ አንድነት ፓርቲን እንዲያወግዝ በተለያዩ ከተሞች ስብሰባና ሰላማዊ ሰልፎችን እንደጠራ አስረድተዋል፡፡ በአንድነት አባላት ቤት የሚደረገው ብርበራ እስከ ምሽት ሊቀጥል እንደሚችልም ለፍኖተ ነፃነት የደረሱ መረጃዎች አመላክተዋል፡፡

 

Source: https://www.facebook.com/MillionsOfVoicesForFreedom


እነ አርቲስት ጀማነሽ ሰለሞን ከነብዩ ኤልያስ አመጣነው ያሉትን መልዕክት ይፋ አደረጉ

0
0

Jemanesh Solomon
ዛሬ በአዲስ አበባ ከተማ ታትሞ የወጣው አዲስ አድማስ ጋዜጣ ወትሮም በአወዛጋቢነቱ የሰነበተውን የነብዩ ኤልያስን ወደ ምድር መምጣትና በአራት ኪሎ እንደሚገኝ የተነገረውን ጉዳይ ይበልጥ እንዲያነጋግር አድርጎታል። ጋዜጣው በዘገባው አርቲስት ጀማነሽ ሰሎሞንን ያካተተው የማህበረ ሥላሴ ዘደቂቀ ኤልያስ አባላት፣ ለፓትርያርኩ ያመጣነውን “የቅዱስ ኤልያስ” መልእክት የሚቀበለን አጥተናል በማለት ለመገናኛ ብዙሃን ይፋ አደረጉ ብሏል። በብሔረ ሕያዋን ይኖራል ከተባለው ነብዩ ኤልያስ ተልከን መልእክታችንን ለኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስትያን ፓትርያርክ አቡነ ማቲያስ እንዳናደርስ የጥበቃ አባላት ከልክለውናል ያሉት የማህበሩ አባላት፤ ከመልዕክቶቹ መካከል ትክክለኛው ሰንበት ቅዳሜ ስለሆነ በእሁድ ፋንታ በብሔራዊ ደረጃ ታውጆ መከበር ይገባዋል የሚል እንደሆነ ተናግረዋል፡፡ “ኦርቶዶክስ” የሚለውን ስያሜ የሚቃወሙት የማህበሩ አባላት፤ “ተዋህዶ” የተሰኘው እምነት ጥንታዊ የጉባኤ እለታትን ጨምሮ አራት የቅዱሳን መታሰቢያ ቀናት በብሔራዊ በዓልነት ለማስከበር ፓትሪያርኩ ከፌደራል መንግስቱ ጋር መነጋገር ይጠበቅባቸዋል ብለዋል፡፡

ቅዱስ ኤልያስ በ2000 ዓ.ም ከመንግስተ ሰማያት ወደ ቅድስት ምድር ወደ ኢትዮጵያ በመምጣት አስተምሯል ያሉት የማህበሩ በቅዱስ ኤልያስ፣ በሄኖክና በመልከፄዴቅ የተባረኩ በመሆናቸው እውቅና ሊሰጣቸው ይገባል ብለዋል፡፡ የዳዊት መዝሙር ላይ በመመስረትና፣ ፓትሪያርኩ የቅዱሳን ሊቃውንት ክብረ በዓላት በብሔራዊ ደረጃ ለማስከበር በቦታው መገኘት ይገባቸዋል በማለት ፓትርያርኩን አሳስበዋል፡፡ የማህበር አባላት በኢትዮጵያ ደረጃ መስከረም 7፣ 12፣ 21 እና የካቲት 21 ብሔራዊ በዓላት እንዲሆኑ ነው ፓትሪያሪኩን ለመጠየቅ የፈለጉት ሲል አዲስ አድማስ ዘገባውን አጠናቋል።

ለግንዛቤ እንዲረዳ ለኤልሳውያን ወይም ለነጀማነሽ ስለሞን አዲስ እምነት ዲያቆን ምህረተአብ አቅርቦት የነበረውን ምላሽ ቪድዮ ከዚህ በታች አቅርበናል።

Health: ፖርኖግራፊ – (ወሲባዊ ምስሎችንና ፊልሞችን የማየት ሱስ)

0
0

ከኢሳያስ ከበደ
(በዘ-ሐበሻ ጋዜጣ ቁጥር 53 ላይ ታትሞ የወጣ)
moral-choices1 የወሲብ ስሜት የሞራል ደንቦችን ሲፈታተን ከዘመን ዘልቋል፡፡ አሁን ያለንበት ዘመን በልቅ የወሲብ ድርጊቶች ምክንያት ሰዎች ለማህበረሰብ ደንቦች ተገዢ እንዳይሆኑ ጋሬጣ የሚሆኑ አማራጮች በሰፊው የሚዳረስበት ጊዜ ነው፡፡ ልቅ የወሲብ ድርጊት አሁን አሁን ስርጭቱ በዓለም ዙርያ ይናኝ እንጂ ከጥንት አንስቶ እስከ 21ኛው ክፍለ ዘመን ድረስ ሰዎች የወሲብ ስሜታቸውን በተለያዩ የጥበብ ስራዎች እንደገለፁ ታሪክም በመዝገቡ አስፍሯል፡፡ ልቅ የወሲብ ድርጊት (ፖርን) ዛሬ ላይ እንደ ኢንዱሰትሪ ከመንሰራፋቱ በፊት የጥንት ዘመን ሰዎች የወሲብ ስሜታቸውን በግብራቸው ሳይሆን በቅርፃ ቅርፅ፣ በስዕል እንዲሁም በስነፅሁፍ ለቀጣይ ትውልድ አስተላልፈዋል፡፡ ለዚህ አይነቱ ድርጊት እማኝ ለመሆን የታሪክ መዘውር ጥንታዊቷ የሮም ግዛት ወደነበረችው ፖምፔይ ይጠቁማል፡፡ ፖምፔይ ከአቅራቢያ ካለው ተራራ በፈነዳ እሳተ ጎመራ መርዛማ አመድ ተውጣ የወደመች ከተማ ናት፡፡ ውድመቱ ካለፈ ከዘመናት በኋላ አርኪዮሎጂስቶች በከተማዋ ፍቅር የሚሰሩ ቅርፃ ቅርፆች እንዲሁም የወሲብ ስሜት ቀስቃሽ ስዕሎች ለማግኘት ችለዋል፡፡ እነዚህ ግኝቶች ለ200 ዓመታት ከሰፊው ህዝብ እይታ ተከልክለው የቆዩ ሲሆን አሁን ላይ በካሊፎርንያ በሚገኝ ሙዝየም ተቀምጠው ይገኛሉ፡፡
አዳም ሄዋንን ካወቃት ዘፍጥረት አንሰቶ እስከ አሁን ሰው በማህበረሰብ የከለከለውን ልቅ የወሲብ ስሜት በተለያዩ ስራዎች አስፍሯል፡፡ ይህም አካሄድ ካለንበት ጊዜ አንስቴ እስከ ምፅአት ቀን እንደሚቀጥል እርግጠኛ የሚያደርገን ደግሞ ኢንተርኔት ዓለምን የመቆጣጠሩ እውነታ ነው፡፡ የኢንተርኔት ግኝት የፓርን ኢንዱስትሪው ትርፋማ እንዲሆን አስችሎትል፡፡ ከልቅ የወሲብ ድርጊት ሽያጭ የሚገኝ ገቢ እንደ ስፖርት ካሉ መዝናኛዎች ከሚገኝ ገቢ በመጠን ይስተካከላል፡፡ እ.ኤ.አ በግንቦት 2001 ዓ.ም የታተመው የኒውዮርክ ታይም መፅሔት ከልቅ የወሲብ ድርጊት ሽያጭ የሚገኘውን ገቢ ‹‹ ወደር የሌለው›› በማለት ገልፆታል፡፡ ፖርን በዓለም ዙሪያ ወደ 54 ቢሊዮን የሚጠጋ ዓመታዊ ትርፍ እንደሚያስገኝ የተለያዩ መረጃዎች ይጠቁማል፡፡ ምንም አይነት ማህበረሰባዊ ቁጥጥርን አሻፈረኝ ካለው ፖርኖግራፊ ጋር የእይታ ትውውቅ የሚደረግበት አማካኝ ዕድሜ 11 ዓመት ነው፡፡ በ21ኛው ክፍለ ዘመን ኢንተርኔት ባለበት ሁሉ ልቅ የወሲብ ድርጊቶችን በቀላሉ ማግኘት ይቻላል፡፡ ኢንተርኔት ለፖርን ኢንዲስትሪው አስተዋፅኦ ቢያደርግም የድርጊቱ ውጥን ሀሳብ ጥንትም ቢሆን በሰዎች ልቦና ተቀብሮ ነበር፡፡ በጥንታዊቷ ፖምፔይ የተገኙት የወሲብ አነቃቂ ቅርፃ ቅርፆች እና ስዕሎች ሁሉንም የማወቅ ጉጉት ያለው የሰው ፍጥረት ልቅ የሆነ የወሲብ ፍላጎት ድሮም ቢሆን አሁን በውስጡ እንዳለ አመላካቾች ናቸውና፡፡
የልቅ ወሲባዊ ድርጊት ታሪካዊ ጉዞ
ከ16ኛው እስከ 18ኛው ክፍለ ዘመን ድረስ በወቅቱ ይከለከል የነበረውን የወሲብ ገደብ በመጋፈጥ ሰዎች የወሲብ ስሜታቸውን በስነፅሁፍ ይገልፁ ነበር፡፡ ለዚህም ጥንታዊት ሮም እና ፈረንሳይ ግንባር ቀደም ሀገራት ናቸው፡፡ የ21ኛው ክፍለ ዘመን ፖርኖግራፊ አቀንቃኝ ወደሆነችው አሜሪካም ወሲብን የሚያነቃቁ ድርሰቶች መግባት የጀመሩት እ.ኤ.አ በ1780 ዓ.ም ነበር፡፡ እ.ኤ.አ በ1789 ዓ.ም የፈረንሳይ አብዮት ፖለቲካዊ ፖርኖግራፊን ይዞ ብቅ አለ፡፡ አብዮቱ ከመቀስቀሱ በፊት የፈረንሳይ ፖለቲከኞች እና ሹማምንቶች የፖርኖግራፊ ተጠቃሞዎች ስለበሩ በወቅቱ የነበረውን የሉዊ 14ኛ ንጉሳዊ አገዛዝ ለማስወገድ የፈረንሳይ ተቃዋሚዎች ንግስት ማርያ አንቶኔት አፀያፊ ወሲብ ስትፈፅም የሚያሳይ በራሪ ወረቀቶችን ያሰራጩ ነበር፡፡ የፈረንሳይ አብዮተኞች ፖርኖግራፊን የንግሥቲቱን ስም ለማጥፋት ተጠቅመውበት እንደነበር ታሪክ ያስረዳል፡፡ ይህንን ተክትሎ በፖርኖግራፊ ታሪክ ትልቅ አስትዋፅኦ ያደረገው ፈረንሳዊ ማርከስ ዴሳዴ የፖርኖግራፊን ገፅታ ከፖለቲካው መድረክ በማውረድ ልቅ ወሲብን ሁሉንም አይነት የሞራል መሰረት መዋጊያ መሳሪያ አደረገው፡፡ ሳዴ በፃፋቸው መፅሐፍቶችም ሰው በተገኘው አጋጣሚ እርካታን በአካሉ መሻት እና ማግኘት እንዳለበት ገልጧል፡፡ የሳዴ እርካታን የመሻት ሂደትም አካላዊ እንግልት እንዲሁም ሰዎችን በማሰቃየት የሚገኝ ደስትን ያካትታል፡፡ ከሳዴ ስምም በመነሳት በ1780 በኋላ የወሲብን እርካታ በአካላዊ እንግልት እንዲሁም በስቃይ ማግኘት የሚፈልገው ሰው ሳዲስት (saddest) በመባል ይጠራ ጀመር፡፡ ሳዴ ይሰብካቸው የነበሩት የወሲብ ሀሳቦች ለዛሬዎቹ የፖርን ፊልሞች ጭብጥ መሰረቶች ናቸው፡፡ ሳደም ፓርኖግራፊን መሰረታዊ የሞራል ደንቦች በገሀድ ለመፃረር የተጠቀመ የመጀመሪያው ሰው ነው፡፡ በማህበረሰብ ሊያስከትሉ የሚችሉትን ተፅዕኖ ከቁጥር በማስገባት ከ18ኛ እስከ 20ኛው ክፍለ ዘመን አጋማሽ የሳዴ ስራዎች ከብዙሀኑ ተሸሽገው ኖረዋል፡፡
የወረቀት መመረትን ተከትሎ ፖርኖግራፊ የህትመት ስራዎች መሰራጨት ጀመረ፡፡ እኤአ በ1970 ዓ.ም ፖርኖግራፊ የዶክመንተሪ ይዘት ባለው ፊልም ተዘጋጅቶ ከሀገረ ዴንማርክ ብቅ አለ፡፡ የአሜሪካውያንን የሞራል ገደብ በመጣስ ‹‹የወሲብ ነፃነት በዴንማርክ›› የሚለው ፊልም በሀገረ አሜሪካ ለእይታ በቃ፡፡ ዴንማርክም ለፖርኖግራፊ እውቅና የሰጠኝ ግንባር ቀደም ሀገር ሆነች፡፡ ቀጥሎ ወጥ ታሪክ ባላቸው የሆሊውድ ፊልሞች ውስጥ ወሲብን ልቅ በሆነ መልኩ ፊልም ውሰጥ ማካተት አስደንጋጭነቱ እየቀነሰ መጣ፡፡ ከ1980 አንስቶ እስከ 21ኛው ክፍለ ዘመን ባለው ጊዜ ፓርኖግራፊ አስገራሚ እድገትን አስመዘገበ፡፡ እኤአ በ1985 ‹‹የእርቃን›› እና የልቅ ወሲብ ገበያው በዓለም አቀፍ ደረጃ 75 ሚሊየን ዶላር ሲያስገባ እኤአ በ2009 ገቢው ወደ 4.9 ቢሊየን ዶላር አሻቀበ፡፡ ፓርኖግራፊም እንደ ፓሜላ አንደረስን ያሉ አሜሪካዊ እንስቶችን በወሲብ ልቅነታቸው በዓለም ዙርያ ዝነኛና ከበርቴ አደረገ፡፡ በኢንተርኔት ዘመን ከሙዚቃ፣ ከመፃህፍት፣ እንዲሁም ከአገልግሎት ሰጪ ድረገፆች ይልቅ የፖርን ድረገፆች በእጥፍ ይጎበኛሉ፡፡
ባለፉት 500 ዓመታት ማህበረሰብ ለፖርን ያለው አመለካከት መቀየሩ፣ የቴክሎጂ እድገትን ተከትሎ ድርጊቱ መስፋፋቱን እንዲሁም የሞራል መሰረቶች ፖርኖግራፊን ለመቆጣጠር እንደተሳናቸው ታሪክ ያስረዳል፡፡ የወሲብ ልቅነት አስደንጋጨ ዕድገት ታሪክ ምን ቢያወሳ እና የሚያስገባውን አህዛዊ ትርፍ መረጃዎች ቢጠቁሙም፣ ፖርኖግራፊ ልንክደው የማንችል አሉታዊ ገፅታ በማህበረሰብ ላይ ያሳድራል፡፡
የልቅ ወሲባዊ ድርጊት አሉታዊ ገፅታዎች የሀሳብ፣ የድርጊት እንዲሁም የምርጫ ነፃነት የካፒታሊዝም መገለጫዎች ናቸው፡፡ የነፃነት ሀሳብ በወሲብ ስሜት ሲገለፅ ያለ ከልካይ ስሜትን በሚያስተናግደው ፓርኖግራፊ ጣሪያውን ይነካል፡፡ በኢንተርኔት ፖርን ብለው ፍለጋ ቢያደርጉ ከ2ሚሊየን በላይ ድረገፅችን ያገኛሉ፡፡ በሀገራችን እነዚህ ድረገፆች ለሰዎች ተደራሽ እንዳይሆኑ የሚደረግ ቁጥጥር ባለመኖሩ ህፃን፣ ወጣት፣ አዋቂ፣ ጎልማሳ፣ እንዲሁም ጤናማ ማህበረሰብ ከመፍጠር አኳያ የሚያበረክተውን አሉታዊ ተፅእኖ ከቁጥር በማስገባት ፓርኖግራፊን ማውገዝ የእያንዳንዳችን ፋንታ ነው፡፡ ካፒታሊዝም የምርጫ ነፃነትን ይሰጣልና፡፡ S

የቅዱስ ዑራኤል ንግሥ ለ10ኛ ጊዜ በሚኒሶታ ተከበረ

0
0

(ዘ-ሐበሻ) ከተመሰረተ አስረኛ ዓመቱን ያከበረው የሚኒሶታው ቅዱስ ዑራኤል ቤ/ክ ዛሬ የቅዱስ ዑራኤልን ዓመታዊ በዓል በደመቀ ሁኔታ አከበረ። በዚህ ለ10ኛ ጊዜ በተከበረው በዓል ላይ ብጹዕ አቡነ ሳሙኤል የዋሽንግተን ዲሲና አካባቢው ሃገረ ስብከት ሊቀጳጳስ፣ ብጹዕ አቡነ ሳዊሮስ የሚኒሶታ፣ የሳውዝ ዳኮትና የኮሎራዶ ሃገረ ስብከት ሊቀጳጳስና፣ ሐዲስ ሐዋርያ አባ ወ/ትንሣኤ አያልነህን ጨምሮ በርከት ያሉ ካህናትና ዲያቆናት እንዲሁም በሚኒሶታና አካባቢው የሚኖሩ ምዕመናን እና የሰንበት ትምህርት ቤት አባላት ተገኝተዋል። በተለይም በዛሬው ዓመታዊ ንግሥ በዓል ላይ በዋልድባ ገዳም እየደረሰ ያለው የአባቶች ስቃይ የተነሳ ሲሆን በዚህም ላይ ከፍተኛ የሆነ የአባቶች ምስክርነት ተሰምቷል። ለምዕመናኑም ግንዛቤ ተሰጥቷል።
በ4ኛው ፓትርያርክ አቡነ መርቆሪዮስ የሚመራውና በሚኒሶታ የዑራኤልና ኪዳነ ምህረትን ደብሎ የያዘው ይኸው ቤተክርስቲያን ለ10ኛ ጊዜ ዑራኤልን ባነገሰበት በዓል ላይ የተገኙት አባቶች ስለሰላም፣ ስለቤተክርስቲያን አንድነትና በተለይም ኢትዮጵያ ውስጥ በየገዳማቱ በአባቶች ላይ እየደረሰ ያለውንና በኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤ/ክ ላይ ስውር እጆች እያደረሱ ያሉት ጥፋቶች ሁሉ ለምዕመናኑ ተገልጿል።
የቤተክርስቲያኑ አስተዳዳሪ ቆሞስ አባ ገብረሚካኤል ተሰማ ለዘ-ሐበሻ እንደገለጹት ነሐሴ 1 (ኦገስት 7) ቀን የሚገባውን የፍስለታ ጾም በማስመልከት በየቀኑ በቅዱስ ዑራኤል ቤ/ክ ቅዳሴ እንደሚኖር ገልጸው ም ዕመናኑ በቅዳሴው ላይ እንዲገኝ ጥሪያቸውን አቅርበዋል። ለፍልሰታ ጾም ፍቺም የኪዳነ ምህረት ዓመታዊ ክብረ በዓል በዚሁ ቤተክርስቲያን እንደሚደረግ አስተዳዳሪው ጨምረው ገልጸዋል።
የዛሬውን በዓል በከፊል የሚያሳይ ቪድዮ ደርሶናል – ተመልከቱት።

የት ይደርሳል የተባለ ጥጃ ወያኔ ግቢ ውስጥ ሲልከሰከስ ታዬ!

0
0

ጦቢያን ገረመው

Haile

ኃይሌ በዜግነት ምክንያት ፕሬዝደንት ይሆናል አይሆንም የሚባለው ቀልድ ጉንጭ አልፋ ነው፡፡ ወቅታዊ ቀልድም ይመስለኛል፡፡ መለስ ዜናዊና በረከት ስምዖን በፍላጎታቸውና በወፍዘራሽ የዜግነት ፍልስፍናቸው ‹ኤርትራዉያን› ሆነው ሲያበቁ ‹የጎረቤት ሀገር ኢትዮጵያን› አንቅጥቅጠው እየመሩ ባሉበት ሁኔታ ኃይሌን ከኢትዮጵያዊነት አንጻር ማማት ለራሱም ሳያስቀው አይቀርም፡፡ ያ ዓይነቱ ጨዋታ የፖለቲካ ጨዋታ ነው፡፡ ‹በእውኑስ አሁን ኢትዮጵያ እየተመራች ያለችው በኢትዮጵያውን ነውን?› ብለንም መልሱ በአንድዬ እጅና በታሪክ ማሕጽን ውስጥ የሚገኝ ጥያቄ መጠየቅ እንችላለን – ለራሳችን፡፡ ኃይሌን በዜግነት ችግር ማንቀራበጥ ለወያኔ ድራማ ማጠናከሪያ ውሻል ማቀበል ይመስለኛል፡፡ አንደኛ ነገር ወያኔ ሕግ ማውጣት እንጂ ማክበር አያውቅበትም፤ እንዲያውም ያቆመው ሕግ የማይጠቅምና በረዳቶቹ ዘንድ ትዝብት ውስጥ የሚጥለው መስሎ ካየው በአንድ አዳር ያን ሕግ ተብዬ ሰርዞ በምትኩ ሌላ ሊያወጣ የሚችል የዘመኑ መንግሥታዊ ጨቡዴ መሆኑ ለማንም ግልጽ ነው፡፡ እናም ችግሩ የዜግነት እንደማይሆን ይገባል ይልቁንስ፡፡ የኃይሌ ሀገርን መምራት ያለመቻል ችግር ያለው ከዜግነት አንጻር ሊመስለኝ አልፈልግም፡፡ ስንትና ስንት የፈጠጠ ጉድለት እያየንበት በዚህ ውሃ የማያነሳ ጉዳይ ጊዜ ማባከኑ በማይሠራ ሕግና ከ‹ተጻፈበት ቀለም› የዘለለ ዋጋ በሌለው ወረቀት ላይ በከንቱ ከመጯጯህ ያለፈ ፋይዳ የለውም፡፡
ከሰሞነኛ የሀገራችንና የዓለማችን አንዳንድ ሥራ ፈት የዜና ማዕከላት ወሬዎች መካከል አንዱ የኃይሌ ገ/ሥላሤ የሥልጣን አራራ መሆኑን በግሌ መረዳን ሳላሳውቅ ወደሁለተኛው አንቀጽ በመግባቴ ይቅርታ እጠይቃለሁ፡፡ እናም በግሌ – ጉዳዩ በቀጥታ እንደሚያገባው አንድ ኢትዮጵያዊ – ስለዚህ መካሪ ያጣ የገንዘብና የሥልጣን በሽተኛ ሰውዬ የሚሰማኝን ጥቂት ነገር ልበል፡፡ ያገባኛል ያልኩት ያለኝ ዜግነት አንድ ብቻ – ያም ኢትዮጵያዊነት ብቻ በመሆኑም ብቻ አይደለም፤ ያገባኛል ያልኩት ከኢትዮጵያ ውጪ ሌላ መመኪያና መኩሪያ ስለሌለኝ ብቻም አይደለም፤ ያገባኛል የምለው ይህን ሰው በሚገባ ስለማውቀው እንኳንስ ሀገርን የመሰለ ትልቅ ነገር ለመምራትና ቤቱንም በአግባቡ ለማስተዳደር የሚያቅተውና በዘመናዊ የቴክሎጂ መሣሪያ ቢመረመር የጤናማነቱ ጉዳይ ቤተሰብ ለመመሥረት ጭምር የማያስቸለው እንደሚሆን በከፍተኛ ደረጃ ስለምጠራጠር ነው – የኔ ‹ሥራ› መጠራጠር ነው – የ‹አልጠረጠርም› ባይ ሥራ ደግሞ ጥርጣሬን ማስወገድ የሚያስችል ማስረጃ ማቅረብና ጠርጣሪን ማሣፈር ነው፡፡ አዎ፣ ደደብን ደደብ ካላሉት ቤተ መንግሥት ውስጥ በማያውቀው ነገር ገብቶ ይፈተፍታል ይባላል፡፡ ኃይሌ እውነቱን ይረዳው – ሕዝቡ አብጠርጥሮ ያውቀዋል – ከዋናው በር እስከመኝታ ቤቱ እናውቃለንና ዝምተኝነታችንን አይበዝብዝብን፤ በሀብቱ ወይም በወያኔያዊ ጥገኝነቱ ፈርተን የማንናገር ከመሰለው ተሳስቷልና ከአሁኑ ይታረም – ቢያንስ እሱና እሱን መሰል ቅሌታሞች እንዲፈነጥዙብን አንፈቅድም – እውነቱን በመናገር የእሱነቱን ማንነት እናጋልጣለን፡፡ እናም ዘመድ ካለው በጊዜ ይምከረውና የሥነ ልቦና ዐዋቂ/ሐኪም እንዲያክመው ያድርግ፤ አለበለዚያ ብዙ ጣጣ ውስጥ ይገባል፤ በእልህ የጀመረውን የዕብድ ውሻ መንገድ እገፋበታለሁ ካለ በግል ሕይወቱ ጭምር እየገባሁ በምዘባርቃቸው አንዳንድ ጉዳዮች በጣም ላስከፋው ከወዲሁ ቃል እገባለሁ፤ ከዛሬ ጀመርኩ፡፡ ይሉኝታ የሚሠራው ይሉኝታ ላለው ነው፤ ከፈጣሪ መንገድ እንዳፈነገጥሁ ይገባኛል – ጊዜ ካለኝ ንስሃ እገባለሁ እንጂ እንዲህ ያለውን መናኛ ስብዕና ከማጋለጥ አልመለስም፡፡ በሚሆነው አዝናለሁ – ምርጫ ግን የለኝም፡፡
እርሱ በኛ ላይ ከሚያደርገው ብልግና ይልቅ የአንድን ሰው ገመና ገሃድ ማውጣትና ሀፍረትን የሚያውቅ ከሆነ በሀፍረት እንዲሸማቀቅ ማድረግ ከተቆርቋሪ ዜጎች ይጠበቃልና የእርሱን ብልግና የምታውቁ ሁሉ ከእንግዲህ አትሳሱለት፤ ለይሁዳ የሚሳሳ አንጀት ሊኖረን አይገባም፡፡ ገና ለገና ባንዲራችንን – ሊያውም ኋላ ኋላ ላይ ኢትዮጵያን በትክክል የማይወክል የወያኔን ደባደቦ ባንዲራ እየመረጠ – አውለብልቧል ብለን እላያችን ላይ ሲያቀረሽ ዝም ማለት የለብንም፡፡ ይሄ ቆሻሻ የውሻ ልጅ በኢትዮጵያማ እንዲህ አይጨማለቅም! የሌሎቹ አነሰንና ደግሞ ይህ ማይም የወያኔ እግር አጣቢ በስማችን ይነግድብን? አላሙዲንና ኃይሌን ለመሰሉ ውሾች – በአእምሮ ሣይሆን በሆድ የሚያስቡ ደንቆሮ ዓሣሞች የሚያዝን ኅሊና የለኝም፡፡ ይቅርታና ምሕረት ሌላ ነው – ሆን ብሎ ሀገርን ለገንዘብና ለዝና እንዲሁም ለሥልጣን የሚሸጥ የዲያብሎስ አጋንንት ግን በምንም መንገድ ሊታለፍ አይገባም፡፡ ወያኔ ጋር እየተሸራሞጡና ሣምባን ከካሊፕሶ እየጨፈሩ ሕይወቴን የቀን ጨለማ እንዲውጠው ያደረጉትን ሁሉ – ማንም ይሁኑ ማን – ምንም ይሁኑ ምን – በተቻለኝ ሁሉ ሌላው ቢቀር በብዕር እዋጋቸዋለሁ፡፡ የነዚህን ሰዎች ግፍና በደል ለመሸፈን የሚሞክር ሁሉ የነሱ ተባባሪና ረዳት ነውና በበኩሌ ጥቁር ውሻ እንዲወልድ እራገማለሁ፤ እናም ተራገምኩ – ‹ይህን መልእክት ሆን ብሎ ያፈነ ወይ ያሳፈነ በዚህ መልእክት ውስጥ የተጠቀሰ የመርገምት ቃል ሁሉ በራሱና በትውልዱ ይድረስ!›፡፡ ከአሁን በኋላ ለኃይሌ የሚራራ አንጀት ያለውና ከእርሱ ጎን የሚቆም ሁሉ ከኢትዮጵያ ጠላቶች ጋር ተባብሮ ታሪክንና ሀገርን ለማጥፋት ከጥልቁ የእሳት ባህር የመጣ እንጂ ሕዝባዊ ወገናዊነት ያለው ጤናማ ዜጋ ሊሆን አይችልምና ኃይሌንና መሰል የወያኔ ቡችሎችን የማይቃወም ከወያኔ አንድ ነው – ስለሆነም እየመጣ ያለው የእሳት ዝናም በእርሱም ላይ ይዝነብ፡፡ ዕድሜውም ልክ እንደወያኔ ሁሉ አጭር ይሁን፤ የወያኔ ጣዕረሞት የርሱም ዕጣፋንታ እንዲሆን ፈቃደ መለኮት ይሁንልኝ – ‹እንዴት? በምን ምክንያት?› እያላችሁ አትጠይቁ (መጠየቅ ያስቀስፋል! Kidding … )- የወያኔ ዕድሜ በሰማያዊ የጊዜ አቆጣጠር በክፍልፋይ ሴከንዶች የምትቆጠር ናት – ወያኔ ጣር ላይ ነው፡፡ ጣር ላይ ያደረሰው የምሥኪኖች ዕንባና የሚዋኝበት የደም ባህር እንጂ የሌላ እንዳይመስላችሁ በተለይ አንዳንዶች በሰው ሥራ ላይ እንዳትመኩ – ማለቴ እንዳትኮፈሱ፡፡ የታዘዘው ኃይል ገና ተገቢ ሥራውን በቅጡ አልጀመረምና! (የነቢይነት ተሰጥዖ የለኝም – እምናገረው የውስጤ የሚነግረኝን እንጂ እንደሁሴን ጅብሪል ፊት ለፊቴ የተሰቀለ ጀንዲ ወይም አንሶላ ላይ የተነጠፉ ቃላተ ትንቢትን እያነበብኩ አይደለም – ስለዚህ ይህን ‹ስሜት ወለድ› ፈለገ-ሃሤት ጠቅሶ ሰውን ማስደሰት እንዳይቻል በማይም ቃሌ ገዝቻለሁ – ቆዳ ታጣቂውና አንበጣ በሊታው ዮሐንስ በባዶ እግሩ በበረሃ እየዞረ ምን ነበር ያለው? … (አሃ፣ ወዴት ጠጋ ጠጋ – የስሙኒ ቲማቲም በኪሎ 25 ብር ገዝተው ‹እየቆረጡ›ና የአንድ ብሩን ነጭ ፊያሽኮ ቪኖ በ45 ብር ገዝተው ‹እየኮመኮሙ› የምን ‹ጊዜው ቀርቧል፤ ንስሃ ግቡ› እያሉ በከተማ በረሃ ባስካርባ እየሄዱ መጮህ ነው?)ዓለም
ኃይሌ ፍጹማዊ ገብጋባ ነው – ከሚቋምጥለት ሥልጣን ጋር ምን አገናኘው እንዳትል – ትስስሩን እናገራለሁ፡፡ ገብጋባነቱ ደግሞ አንድና ሁለት ብቻ ሣይሆን ዓለም የምትጠቀማቸው ቁጥሮች አይገልጹትም፡፡ እንዴ! ለመሆኑ ኃይሌ ከነአካቴው ሰው ነው ማለትስ ይቻላልን? ቀጣዩን የአንዲት ቀን ገጠመኝ (anecdotal episode) እዩና ራሳችሁ ፍረዱ፡፡ ይህ ሰው ልምራችሁ ሲልም ይታያችሁ፡፡
ኃይሌ ይህን እውነተኛ ታሪክ እንዲያስታውስ ወዳጆቹ ንገሩት – የዚህን ደብዳቤም ግልባጭ ላኩለት፡፡ አንድ ወቅት ወደርሱ ቤት የሚገባ የውሃ ጉድጓድ ይቆፈር ነበር፡፡ የቁፋሮው ሥራ እየተካሄደ ሳለ ከሚቆፍሩት ወዛደሮች አንድኛው በናዳ ሕይወቱ ያልፋል፡፡ ያን ሬሣ ወዳገሩ (ወደጎጃም) ለመላክ ሥራውን ይቆጣጠር በነበረ አንድ ጓደኛየ አማካይነት የአካባቢው ማኅበረሰብ ገንዘብ እንዲያዋጣ ይጠየቃል፡፡ ቦታው ቦሌ ነው፡፡ ሁሉም የቻለውን ረዳ፡፡ ያ ከዚያን ጊዜ በፊት ኃይሌን ከቆንቋናነት አንጻር የማያውቀው ጓደኛየ ኃይሌን ከቤቱ አስጠርቶ ችግሩን ይገልጥለትና የረድኤት እጁን እንዲዘረጋ ይጠይቀዋል፡፡ ሀገርና ወገን ወዳዱ ኃይሌ፣ በኦሎምፒክ ሜዳዎች ባንዲራ ሲሰቀል የዐዞ ዕንባውን የሚረጨው አስመሳዩ ኃይሌ ወዲያውኑ ሃያ ብር ያወጣና ይሰጣል፡፡ ጓደኛየ ክው ብሎ ይደነግጣል – እዚያ አካባቢ የነበሩ ወዛደሮችና አላፊ አግዳሚ ተራና በጣም ድሃ ዜጎች ከዚያ ገንዘብ እጅግ የሚበልጥ ሰጥተዋልና የጓደኛየ ድንጋጤ የሞት ያህል ሆኖ አጽናኝ አስፈልጎት እንደነበር ከብዙ ዓመታት በኋላም አሁን ድረስ እያንዘረዘረው ያስታውሰዋል፡፡ ጓደኛየ ሲረጋጋ “ምነው ኃይሌ? ይህን ያህልማ እኔም አያቅተኝም፤ ከአንተ እኮ የምንጠብቀው … ይህ ልጅ እኮ ሲሰራ የነበረው ወዳንተ ቤት ይገባ በነበረ መስመር ነው፡፡ ካንተማ …” በማለት ሲወተውተው “እንዴ – ደም ተፍቼ እኮ ነው የማገኘው፤ መሬት ወድቆ እኮ አላገኘሁትም …”ብሎ እያጉመተመተ ቤቱ ይገባና ያቺን ሃያ ብር አስቀርቶ 200 ብር ይሰጠዋል፡፡ ኃይሌ እኮ ለጫማ ጠራጊ አንድ ብር ሰጥቶ ሃያ አምስት ሣንቲም መልስ ለመቀበል ዝርዝር እስኪገኝ ድረስ ግማሽ ሰዓት የሚጠብቅ እጅግ ሰፍሳፋና ‹ሀገርና ወገን ወዳድ› ብርቅዬ ዜጋ ነው፡፡ …
መስጠት አለመስጠት የግል ጉዳይ ነው – በመሠረቱ፡፡ እኔ የምለው ግን የዚህ ዓይነት የተለዬ ጋብሮቭ ኢትዮጵያን ልምራ ብሎ መናገር ሳይሆን ማሰብም አይገባውም፡፡ ይቅርና በወያኔ የውሸት ሥልጣን፣ በነገይቱ ኢትዮጵያም ቢሆን ማሰብም የለበትም፡፡ አመራር ከቸርነት ይጀምራል፤ ያለውን አለምክንያት ይበትን ወይ ይዝራ ማለት አይደለም – ግን እስከዚህን አስተዛዛቢና አንጀትን እስከወዲያኛው የሚቆርጥ ደረጃ የሚንገበገብ ሰው የቤቱንም ቆሎና ስኳር እየቆጠረ – የሞሰብ እንጀራ ላይ በሣር ምልክት እያደረገ በሻይሎካዊ ባሕርይ ሌሎችን ሰላም መንሳቱ አይቀርምና ወደ ቁጩም ሆነ ወደእውነተኛ የሥልጣን ወንበር ሊጠጋ አይገባውም፡፡ ከነብሂሉ ‹ሆዳም ሰው ፍቅር አያውቅም›፡፡ ገብጋባ ሰው ሆዳም ነው፤ ሆዳም ሰው ገብጋባ ነው፤ ገብጋባ ሰው ራሱን አይወድም፤ ገብጋባ ሰው ሰውን አይወድም፤ ገብጋባ ሰው ሀገር አያውቅም፤ ገብጋባ ሰው ፍቅር አያውቅም፤ ሆዳም ሰው ለሆዱ ሲል ሀገሩንም ወገኑንም ቤተሰቡንም ይሸጣል፡፡ ኃይሌ ለገንዘብና ለዝና ሲል ዓለምን ሸጦኣል ፤ ዓለምም ዘወርዋራ ናትና ፊቷን አዞረችበት – በመጨረሻም የሀብትና የዝና ጥሙ አንጎሉ ላይ ሲያናፍልበት ተመልክታ ብታስጠነቅቀውም ሊሰማት ባለመቻሉ እሷም ናቀችው – ከሕዝብ ጋር ሲላተም እያየችም አላዘነችለትም፤ በቂ የጥሞና ጊዜ ስጥታው ነበርና – ዓለም እንዲህ ነች፤ ሕይወትም፡፡ ተፈጥሮው ለአመራር ሳይሆን ገንዘብና ዝና ለማሳደድ ነው – ኃይሌ ገንዘብና ዝና አይጠግብም – እሱን መሰሎችም እንዲሁ፡፡ ኃይሌ ያቋቋመው በጎ አድራጎት አለ? ኃይሌ እንዲህ ያለ መልካም ነገር ለእገሌ ሠራ ተብሎ ያውቃል? በመጀመሪያ ለዕርዳታና ለመሰል የበጎ አድራጎት ሥራዎች ወደኃይሌ ቤት የሚሄድ ሰው ያለም አይመስለኝም – ሁሉም ስለሚያውቀው – ማን አፉን ያበላሻል? ለወትሮ ጅብ ነበር ወደማያውቁት ሀገር ሄዶ ቁርበት አንጥፉልኝ የሚል፤ ዛሬ ደግሞ ዘመን ተዛወረና ደደቡና ማይሙ ኃይሌ በሚታወቅለት ለፍዳዳ አንደበቱ የሕዝብን የነጻነት ትግል ለማኮላሸት ከሀገር መሠሪ ጠላቶች ጋር ይለፋደድ ያዘ፡፡ ‹ልጅ አይውጣለት› ብዬ አልረግመው ነገር ሆኖብኝ ተቸገርኩ እንጂ ሰውዬው ብዙ ያናግራል፡፡ ብቻ እግዜር ይይለት – ዕድሜውንም እንደሚያመልክበት እንደመለስ ያድርገው! በቃ፡፡ ከጠሉ ወዲያ ልምምጥ የለም፤ የኛ ነበር – የኛነት አስጠላው – የዝና ሰይጣናዊ መንፈስ እኛን እንዲጠየፍ አስገደደው – በኛም ላይ ሽንቱንና ለከት ያጣ ቅርሻቱን ይለቅብን ጀመረ፡፡ ስለዚህ ሞቱን እንጂ ብልግናውን ላለማየት ቆርጫለሁ – ይሆናል፡፡ እንኳን ኃይሌ ጎብላላዎቹ ሐምሌና ነሐሴም ያልፋሉ፡፡
የኃይሌ ተፈጥሮ ሀገርን መምራት ሳይሆን ሮጦ የራሱን ስምና የሀገርን ስም ማስጠራት ነው፡፡ ሁሉም ሰው የየራሱ ተፈጥሮ አለው፡፡ ለመሪነት የራሱ የሆነ ግርማ ሞገስና የዕውቀት ደረጃ አለው – እንዳሁኑም የወያኔ ዘመንም ሆነ እንዳለፉት መሪር አገዛዞች ሳይሆን እንደጥንቱ አፍላጦናዊ ፍልስፍና፡፡ ማይሙ ኃይሌ ተፈጥሮ የለገሰችው ችሎታ መሮጥን ነው – በቃ፤ እግርና ጭንቅላት ደግሞ ለዬቅል ናቸው – በአቀማመጣቸው እንኳን ተቃራኒዎች መሆናቸውን ያጤኗል፡፡ ከተፈጥሮ ችሎታው ከሩጫ አልፎ መሪ አድርጉኝ ቢል ግን ወጥ መርገጥና አሳዳጊ የበደለው መሆኑን በይፋ ማሳወቅ ነው – ለወያኔ ሥልጣን አይመጥንም ማለት እንዳልፈለግሁ ግን አስረግጬ መናገር እፈልጋለሁ – ለወያኔ ሹመት በትንሹ ግዑዝ ድንጋይ መሆን ከበቂ በላይ ነው – አምባሳደር ለመቀበልና ለመሸኘት ደግሞ እንደራስ ሆቴል አንበሣ በምሥል መልክ ወንበር ላይ የሚዘፈዘፍ ግርማ ወልደጊዮርጊሳዊ ጥውርም ሲበዛ ነው፡፡ ኃይሌን በሚመለከት አጥንቴ ድረስ ዘልቆ ክፉኛ የተሰማኝ የኢትዮጵያን ሕዝብ መናቁና ሀገር ሻጭ ወያኔን መጠጋቱ ነው – ምንም ነገር ሳይቸግረውና ማይማዊ ደደብነቱ አስገድዶት (በነገራችን ላይ እንደወያኔዎች ሁሉ በሰይጣናዊነት እንደሚታማም አውቃለሁ – በማስጠንቆል የደረሰበትን የሀብትና የዝና ጣሪያ የማናውቅ መስሎትም ከሆነ ተዘናግቷልና እንደምናውቅ ይወቅ፤ ከተመቸኝና ከፈለግሁ ወደፊት በዚህ ጉዳይ ዙሪያ እመለስበታለሁ)፡፡ እንኳንስ እርሱ እኔ ራሴ – ኃይሌ ንፍጡን እያዝረከረከ ደብተሮቹን በጉያው ወትፎ ወዳልጨረሰው ትምህርቱ ይሄድ በነበረበት ሰዓት ከፖለቲካው ባልራቀ ሁኔታ ሀገሬን አገለግል የነበርኩትና በመቶዎች የሚቆጠሩ ማኅበራዊና ፖለቲካዊ ይዘት ያላቸው መጣጥፎችን ለሀገሬ ያበረከትኩት ሰውዬ ለቀበሌ አመራር እንኳን እበቃለሁ ብዬ አላስብም፤ ምክንያቱም ተፈጥሮየ ለአመራር ሳይሆን ለመጻፍና ምናልባትም ለማላውቀው ለሌላ ነገር ነው፡፡ ምቹ ሁኔታ ተፈጠረልኝ ብዬ እንደኃይሌ ‹ለዚህ ቦታ ምረጡኝ› ብል መናገሩንና መወዳደሩን እንደምችል ባውቅም ካለተፈጥሮ ዝንባሌና ችሎታ ገብቼ መፈትፈቱ ግን የኋላ ኋላ ችግር እንደሚያመጣብኝ እረዳለሁና አልሞክረውም፡፡ ይህን የምለው ለጊዜው ሌላ እውነተኛ ማነጻጸሪያ ስላጣሁና እውነቴንም ስለሆነ ነው፤ ጊዜ ሰጠኝ ተብሎ ወደአንድ ነገር ቢሞጀሩበት ችግር ነው – የግብጹ ሞሐመድ ሞርሲን ልብ ይሏል – የተፈጥሮ ጥሪን መረዳት ተገቢ ነው ወንድሞቼ እንዲሁም እህቶቼ፡፡ እናም ኃይሌ መቶ ሀገር ቀርቶ አንድ ሺህ ሀገር ቢዞርም በኢሣት እንደሰማሁት አዟዟሩ የሩጫ እንጂ ፖለቲካዊ የሥራ ጉብኝት ባለመሆኑ ዙረቱ እንደተባለው ዕቃ ለመሸመትና ያማረ ሆቴል ተከራይቶ ለመንፈላሰስ ካልሆነ በስተቀር ለምንም ዓይነት የፖለቲካ ተሹዋሚነት አያበቃውም፡፡ ይህ ሰው ጭንቅላት የሚባል ነገር በጭራሽ ስለሌለው እንጂ – እንደእንስሳ ሽምጥ ለመጋለብ ከሚጠቅም ደመነፍሳዊ አንጎል በስተቀር ማለት ነው – ትንጥዬ አንጎል ብትኖረው ኖሮ ወደዚህ ቅሌትና ውርደት አይገባም ነበር፡፡ በደደብነቱ ሳቢያ ልቦናው ታውሮበት እንጂ እኔና እርሱ እንደዮሐንስ መጥምቁ አባባል የጫማቸውን ማሠሪያ ለማሰር ወይ ለመፍታት የማንበቃ ስንትና ስንት ዶክተሮችና ፕሮፌሰሮች ኢትዮጵያውን ቀኒቱን እየተጠባበቁ ናቸው – በበሣል አመራራቸው እንደእስራኤል በጥቂት ዓመታት ውስጥ ኢትዮጵያን ሌሎች ሀገሮች ወደደረሱበት የሥልጣኔና የዕድገት ማማ ለማድረስ(አባብሌ ዲግሪው ላይ አለመሆኑን ‹ፕሊዝ› ተገንዘቡልኝ – ለዲግሪ ለዲግሪውማ ‹ፕሮፌሰሮች› ክንፈ አብርሃምና አንድርያስ እሼቴስ ነበሩን አይደል? በአካልም በመንፈስም በኅሊናም ሙታን ሆነው ሀገር ሻጮች ጋር ተባበሩብን እንጂ)፡፡ ከዚህ ሰው ሳይሆን ምቹ ሁኔታን የማጣታችን ሁኔታ አኳያ የዚህን ንፍጣም ሰውዬ ምኞትና የሕጻን ፍላጎት የሚመስል ጤንነት የጎደለው ቅዠት ስታዘብ አንዳች የመደፈር ጸጸት ይወረኛል፤ በምትንቀው መናኛ ሰው እንደመደፈር ያለ ደግሞ የጸጸት መንስኤ የለም – ደግሜ ልራገም መሰለኝ – የሥራውን ይስጠው፤ እሱ ሕዝብን እንደናቀ በዓለምም እንዳስገመተን ሞት ግን ውለታ ይዋልልንና ንቆ አይተወው፡፡ ራስን ያለማወቅ ችግር – እርግጥ ነው – የዓለማችን ራስ ምታት መሆኑ የታወቀ ነው፡፡ ይሁንና ራስን አለማወቅ የፈለገውን ያህል ችግር ያስከትል እንጂ እንደኃይሌ ያለ ሰው በምናውቅለት የሥራና የትምህርት ወይም የችሎታና የልምድ ታሪክ ከመሬት ተነስቶ የጠላት መሣሪያ ልሁን ብሎ መነሳቱ ዕብደት ካልሆነ ሌላ ምንም ሊሆን አይችልም፡፡
‹ምላሴ ጥቁር ነው፤› እርግማኔ አይደርስም አልልም፡፡ በሥርዓት ደረጃ እየዘገየብኝ ተቸገርኩ እንጂ በግለሰብ ደረጃ እርግማኖቼ ዒላማዎቻቸውን መትተው ወደሰገባቸው የሚመለሱባቸውን ጊዜያት ማስታወስ አይከብደኝም፡፡ አበበ ገላው በመብረቃዊ የቁጣ ድምጹ የተሸሸገና በያዝ ለቀቅ የፖሊስና ሌባ ጨዋታ ከሟች ጋር ድብብቆሽ ይጫወት የነበረን ነቀርሣ አፋፍሞ የመለስን ሞት ማፋጠኑ አይዘነጋም፡፡ በዚያም ምክንያት የጎጃም ባላገር እንዲህ ብሎ ስንኝ መቋጠሩ በ‹ኢቲቪና በኢትዮጵያ ኤፍ ኤሞች› በስፋት ተዘግቧል፡፡
ሽጉጥ አልታጠቀ መትረየስ የለው፤
ባንደበቱ ገዳይ አበበ ገላው፡፡

እኔም በእርግማን ሰው መግደሌ ይፋ ሆኖ ወደሕዝብ ጆሮ የሚደርስልኝ ከሆነ ያገሬ ባላገር እንዲህ ብሎ ሳይቀኝልኝ እንደማይቀር ተስፋ አደርጋለሁ፤ ምኞት መቼም አይከለከልም፡፡

ሞይዘር አልታጠቀ ፊሻሌ የለው፤
በጠሎቱ ገዳይ ጦቢያን ገረመው፡፡

ስለዚህ ኃይሌን እረግሜያለሁና ‹ከኔ እርግማን› ነጻ መውጣት ከፈለገ አሁኑኑ ይቅርታ ጠይቆ ከ‹ውድድሩ› ይውጣና አርፎ ሌላ የሚችለውንና የሚገባውን ሥራ መሥራቱን ይቀጥል፡፡ በበኩሌ ጦሬን ሰክቻለሁ – በፈጣሪ ፊት ተንበርክኬ የእርሱን መጨረሻ እንዲያሳየኝ በዕንባ ጭምር ጠምጄ ይዠዋለሁ – ሌሎችም ዕርዱኝ – እንረዳዳና ይህን ተናግሮ አናጋሪ የወያኔ ዕብድ ውሻ እናስወግድ – የተከፋች ‹አብዮት ልጇን› እንደምትበላም እናሳየው፡፡ መዳኛው አንድና አንድ ብቻ ነው – ያም ተጸጽቶ ሕዝብንም ይቅርታ ጠይቆ መመለስ ብቻ ነው(በወያኔ ትዕዛዝ ወደ አሥመራ ተልኮ ሻዕቢያ ሥር በመደፋት የአማራውን ሕዝብ ለውርደት የዳረገው ንጉሤ አስገልጥ(?) የተባለ ቀልማዳ ከሃዲ እንዴት እንደሞተና ሕዝብ አድሞበት ሬሣው በኩሊ እንደተቀበረ ልብ ይሏል፤ ሕዝብ ከጠላ መድረሻ የለም – በተለይ የኢትዮጵያ! ያቆየንና ገና ብዙ እናያለን ውድ ወርቃማ ኢትዮጵያውያን!) ፡፡ ይህን ደግሞ ይወቅ – ከተገፋና በበደል ብዛት ከሚንተከተክ አእምሮ ኃይል ይመነጫል፤ ያ ኃይል ደግሞ አጥፊም አልሚም ሊሆን ይችላል – ጦርም ዳቦም ከአእምሮ ይፈልቃል፡፡ እየተረጋገምን ዘር ከምናጠፋ እየተሳሰብን ዘር ብናለማ ይሻላልና ይህን መልእክቴን – ሳታናንቁብኝ – ለርሱው ለደንቆሮው ኃይሌ አድርሱልኝ – ሁኔታዎች ቢመቻቹ በአካል ባገኘውና እስከዶቃ ማሰሪያው ብነግረው በወደድኩ – ግን … ፡፡ (እንዳስፈላጊነቱ እቀጥላለሁ!)

የዘመኑ መንፈስ (በእውቀቱ ስዩም)

0
0

beweketu

ባገራችን ባሁኑ ጊዜ ብዙ ተከታይ ያለው ሃይማኖት ብሄርተኝነት ይባላል፡፡የብሄርተኝነት ምእመን ከሆንክ የነፍስ አባት ይኖርሀል፣በጭፍን የምትቀበለው ቀኖና ይኖርሀል፣ነገ የምትገባባት የተስፋ ምድር ይኖርሀል፣ከሁሉ በላይ ደግሞ ብርቱ ችግርህን የምትደፈድፍበት የመስዋእት በግ ይኖርሀል፡፡

ሃይማኖቶች ምእመናንን ብቻ ሳይሆን መናፍቃንንም ያፈራሉ፡፡ብሄርተኞች በስሜት የሚነድደውን ምእመን ብቻ ሳይሆን የኔ ቢጤውን መነፍቅም እንደሚያፈሩ አንርሳ፡፡በነገራችን ላይ ሃይማኖትን መካድ ማለት ሃይማኖት የሚያነሳቸውን አብይ ጥያቄዎች መካድ ማለት አይደለም፡፡እንዲሁም፣ ብሄርተኝነትን መካድ ማለት የኢትዮጵያን ብሄር ብሄረሰቦች ህልውና መካድ ማለት አይደለም፡፡በዚህ ጉዳይ ፣መናፍቅ መሆን ማለት፣ የብሄርተኛ ነቢያት ሰለ ጭቆና ስለ ነጻነት ብሎም ስለ ኢትዮጵያዊነት የሚያቀርቡትን አጉል እምነት መጠራጠር ማለት ነው፡፡

ከኢትዮጵያዊነት እንጀምር፡፡

ከዘመናችን የብሔርተኝነት ነቢያት አንዱ ጃዋር መሐመድ በቅርቡ ከእንቁ መጽሔት ጋር ባደረገው ቃለመጠይቅ ላይ ስለኢትዮጵያዊነት የሚከተለውን ይላል፡፡

‹‹…ኢትዮጵያን የመሠረታት የሶሰትዮሽ ጦርነት ግብግብ ነው፡፡በአማራው፣በኦሮሞው፣በትግሬው ግብግብ ውስጥ ወደ መጨረሻ ላይ በአመራር ስር የበላይነቱን የያዘው አማራው ነበር፡፡በዚህ የተነሳ አሁን የምናያት ኢትዮጵያ ማንነቷ በአማራ ባህላዊ ሥርጭት እና በአማራ ፖለቲካ የተገነባች ነች፡፡…የኢትዮጵያ አገራዊ ማንነት የምንለው የአማራ ባህላዊ ማንነት ነው››

ጃዋር የኢትዮጵያን መሠረት የሦስት ብሄረሰቦች የስልጣን ግብግብ አድርጎ ወስኖታል፡፡ በመጀመርያ፣ ሌሎች ብሄረሰቦች በግብግቡ ተሳትፎ እንዳልነበራቸው አድርጎ ማቅረቡ አንድ

Bewketu Seyoum is a young Ethiopian writer
በእውቀቱ ሥዩም
ጉድለት ነው፡፡ ግን ዋናው ቁምነገር ይሄ አይደለም፡፡ ኢትዮጵያ የግጭት ውጤት ብቻ እንደሆነች አድርጎ ማቅረቡ ነው ትልቁ ስሕተት፡፡ ሲጀምር፣ የግብግብ ታሪክ መሠረት ይንዳል እንጂ መሠረት አይገነባም፡፡ እንደኔ ግምት፣የኢትዮጵያ መሠረት የሆነው ብሄረሰቦች ለጋራ ሕልውና ሲሉ የሚያደርጉት የመደጋገፍ ታሪክ ነው፡፡

ዛሬ ዛሬ፣ ታሪክ ከላሾች፣የብሄሮችን የ‹‹ግብግብ››ታሪክ ሞቅ አድርገው፣አኳሽተው ሲጽፉ፣የብሄሮች መደጋገፍ ታሪክን ግን ቸል ይሉታል፡፡ አለያም እጅግ በቀዘቀዘ ስሜት፣ በጥቂት መስመሮች ብቻ ጨረፍ አድርገው ያልፉታል፡፡ለነገሩ፣ከፋፋይነትን ብቸኛ ያስተዳደር ፈሊጥ አድርጎ የሚቆጥር ሰው በታሪክ ገጾች ውስጥ መመልከት የሚፈልገው ክፍፍልን ብቻ ነው፡፡ታሪክ ግን ብዙ በጎ የትብብር ገጠመኞችን መዝግቧል፡፡ለምሳሌ ጀግናው አጼ ዮሐንስ አራተኛ በበዛሬይቱ ኤርትራ የግብጽን ወራሪ ጦር ድል የነሡት የትግራይ ጀግኖችን ብቻ አሠልፈው አልነበረም፡፡ በዚህ ጦርነት ከግብጽ ጎን ሆኖ፣የተዋጋው አሜሪካዊው ጋዜጠኛ ዊልያም ዴይ እንደመሠከረው ወልቃይቶች፣ጥልጣል የተባሉ የአፋር ንኡስ ክፍሎች፣የወረኢሉ ኦሮሞዎች ለንጉሰነገስቱ ድጋፍ ለማድረግ ተሸቀዳድመዋል፡፡በራስ ወሌ የሚመሩ የአማራ ወታደሮች ተሳትፈዋል፡፡የጎንደር ቀሳውስት ለጦርነቱ ድጋፍ ለማድረግ አድዋ ገብተዋል፡፡ የጎጃሙ ራስ አዳል የደርሼልሀለሁ አለኝታቸውን አሳይተዋል፡፡ የሸዋው ንጉስ ምኒልክ ሳይቀር በመቶ የሚቆጠሩ በቅሎዎችንና ማበረታቻ ልከዋል፡፡ ዝርዝሩን ማንበብ ለሚፈልግ Muslim Egypt Christian Abyssinia የተባለውን የዚህ ደራሲ ማስታወሻ ገጽ 291-292 ያንብብ፡፡ መጽሐፉን በኢንተርኔት ቤተ-መጻህፍት ውስጥ በብላሽ ማግኘት ይቻላል፡፡

ከተለያየ መአዘን የመጡ እኒህ ኢትዮጵያውን ከዘመቻው የሚያገኙት ድልን ብቻ አልነበረም፡፡ በዘመቻ ወቅት ባህል ይዋዋሳሉ፣ቃላት ይወራረሳሉ፣ ስንቅ ያዋጣሉ፣ ልምድ ይለዋወጣሉ፡፡ በሂደት ተቃራኒ ከሚመስሉ ልማዶች የነጠረ ኢትዮጵያዊ ባህል እንደ አረቄ ይወጣል፡፡ ይህን በመዋጮ የተገኘ ባህል ‹‹የአማራ ባህል ››ብሎ ማጥበብ የጸና ድጋፍ ያለው አይመስለኝም፡፡

ጃዋር‹‹አሁን የምናያት ኢትዮጵያ ማንነቷ በአማራ ባህላዊ ሥርጭትና በአማራ ፖለቲካ የተገነባች ነች›› በማለት ሳይወሰን ‹‹የኢትዮጵያ አገራዊ መለያ ማንነት የምንለው አማራ ብሄራዊ ማንነት ነው›› ሲል ይጨምራል፡፡ ጎበዝ ኧረ በህግ አምላክ!!! የኢትዮጵያ ባህልኮ ካንድ አለት የተጠረበ ሕንጻ አይደለም፡፡ ከብዙ የመዋጮ ጡቦች የተገነባ ነው፡፡ ጃዋር እያንዳንዱን ጡብ ቀርቦ ቢመረምረው እዚህ የደረሰበት እርግጠኝነት ውስጥ የሚደርስ አይመስለኝም፡፡

እስቲ ከደቃቅ ምሳሌ እንጀምር፡፡ ኢትዮጵያን የማስተዋወቅ ስራ ሲሠራ አስቀድሞ የሚመጣው የቡና ስነ-ስራታችን ነው፡፡ አንዲት ጠይም ፣ባለሹርባ ሴት፣ያበሻ ቀሚስ ለብሳ ቡና ስትቀዳ የሚያሳይ ምስል በየቦታው ማየት የተለመደ ነው፡፡ይህ ችክ ያለ ምስል በስነ-ስእል ብቻ የተወሰነ አይደለም፡፡ ቢዮንሴና ጆን ኬሪ አገራችንን በጎበኙበት ሰአት የቡና ስነስርአት ተሳታፊ እንዲሆኑ ተደርጓል፡፡ ይህ ማለት የውጭ እንግዳ የቡና ስርአታችንን እንደ ኢትዮጵየዊ መለዮ እንዲመዘግብልን ፈልገናል ማለት ነው፡፡ ለዋለልኝ መኮንን እና ለጃዋር መሀመድ ይህ የአማራ ባህል መሆን አለበት፡፡ በመጀመሪያ እይታ ይመስላል፡፡ ጉዱ ዝርዝሩ ላይ ነው፡፡ የሴትዮዋ ሹርባ ከሐማሴን ወይም ከተንቤን ሴቶች ልማድ ጋር ስምም ነው፡፡ ያበሻ ቀሚሱን የሽሮሜዳ ጋሞ የሸመነው ሊሆን ይችላል፡፡ ጀበናው የጂማ ሙስሊም ኦሮሞዎች ያስተዋወቁት ነው፡፡ አቦል ቶና በረካ አረብኛ ወይም የተወላገደ አረብኛ የተገኙ ቃላት ናቸው፡፡ ዛሬ በክርስቶስ ትንሳኤ በአል በሉባንጃ የሚታጀብ ቡና የማያፈላ ክርስትያን ኢትዮጵያዊ ማግኘት ይከብዳል፡፡ ከጥቂት መቶ አመታት በፊት ግን ቡና የእስላም ልማድ ተደርጎ ይቆጠር ነበር፡፡ የቡና ትርኢት የሙስሊም አበው በኢትዮጵያ ባህል ላይ የጨመሩት በጎ መዋጮ እድርገን ልንቆጥረው እንችላለን፡፡ ኢትዮጵያ ጊዜ በተባለው አናጢ ከብዙ ጡቦች የተገነባች ናት የምንለው ለዚህ ነው፡፡

ጃዋር አማራው የራሱን ባህል በኦሮሞው ላይ እንደጫነ ሲያምን ተገላቢጦሹ ያለው አይታየውም፡፡ ኦሮሞ በረጅም ዘመን፣በሠፊ ምድር፣ ሰፍሮ የመኖሩን ያክል በጎረቤቶቹና በወደረኞቹ ላይ የባህል ተጽእኖ አላሳደረም ማለት ብርቱ ባህል የለውም ከማለት አይለይም፡፡ ባገራችን ዋና ዋናዎቹ የባህል ቀራጺዎች ጦርነትና ሐይማኖት ናቸው፡፡ ለምሳሌ ፣ጀግኖችን እና ነገስታትን አባ በዝብዝ አባ ታጠቅ፣ አባ ዳኘው አባ ነጋ ወዘተ እያሉ መሰየም ገናና ኢትዮጵያዊ ባህል መሆኑን ብዙዎቻችን እናውቃለን፡፡ ብዙዎቻችን የማናውቀው ይህንን ባህል ያስተዋወቁት ለግማሽ ምእተአመት ያክል ኢትዮጵያን ያስተዳደሩት የየጁ ኦሮሞዎች መሆናቸውን ነው፡፡ ብላቴን ጌታ ማህተመ ሥላሴ ወልደ መስቀል ቼ በለው በተሰኘው መጽሐፋቸው ይህንን እንዲህ በማለት ያረጋግጣሉ-

‹‹ነገስታቱ በ‹‹አባ›› ወይም የእገሌ ባለቤት በሚል ቅጽል ስም መጥራት የጀመሩት የኦሮሞዎችን ወይም የወረሸሆችን ልምድ በመከተል ነው ከ1838 ዓም ወዲህ እንደሆነ ታሪክ ይነግረናል፡፡ ወትሮ ግን በተለይም 1474-1713 ዓም ባለው ጊዜ ውስጥ ቅብዓ መንግሥቱ በሚደረግላቸው ሰአት ይወጣላችው የነበረው የግርማ ስም ወይም ስመ መንግስት ‹‹ሰገድ›› የሚል ኃይለቃል በመጨመር እንደነበር ቀጥሎ ያለው ያረጋግጣል፡፡ ወናገድ ሰገድ፣ አጽናፍ ሰገድ፣ አድማስ ሰገድ፣ መለክ ሰገድ፣አድያም ሰገድ ሉል ሰገድ››በማለት ይዘረዝራሉ፡፡

ከጥቅሱ ሦስት ፍሬ ነገሮችን መረዳት ይቻላል፡፡

1- ይህ ባህል ባንድ የዘመን ምዕራፍ ላይ ከኦሮሞ ብሄረሰብ የመነጨ የኢትዮጵያ ባህል ነው፡፡

2- ባህሉ ብርቱ ተጽእኖ ከመፍጠሩ የተነሳ አማራና ትግራይ ነገስታት ለረጅም ዘመን ይጠቀሙበት የነበረውን የስያሜ ዘይቤ ሽሯል፡፡

3- አማራው ታሪክ ጸሀፊ ለባህሉ አስተዋዋቂዎች የባለቤትነት እውቅና ሰጥተዋል፡፡

በሃይማኖት ረገድም ተመሳሳይ ነገር ነው የሚገጥመን፡፡ ለምሳሌ አቴቴ የሚለውን ቃል ደስታ ተክለወልድ ሲተረጉሙ ‹‹ዛር፣በሴት ስም የምትጠራ፣ ውቃቤ ፣ አማሮች ከኦሮሞዎች የወረሷት ጨሌ የሚያጠልቁላት አቴቴ ጊንቢ ሐራ አቴቴ ዱላ እያሉ እንቀት የሚቀቅሉላት አምልኮ ባእድ፣ትርጓሜ ጠባቂ ማለት ነው››ይላሉ፡፡

‹‹አምልኮ ባእድ ››የሚለውን አሉታዊ ሐረግ፣የክርስትያን አድልኦ ያለበት ፍርድ አድርገን እንለፈው፡፡ ዋናው ፍሬ ነገር፣ የአሮሞው ባህል በአማራው ባህል ላይ ተጽእኖ ማሳደሩን ማወቃችን ነው፡፡ ይህም አንዱ ብሄረሰብ ሁልጊዜ ጫኝ ፣ ሌላው ብሄረሰብ ሁልጊዜ ተሸካሚ እንደነበረ አድርገው ሊነግሩን የሚፈልጉትን ሰዎች ያስተባብላል፡፡ በሁለቱ ግዙፍ ብሄረሰቦች መካከል የነበረው ግኑኝነት የእኩዮች ልውውጥ ነው፡፡ የባህሎች ውርርስ ነው ማለት እንችላለን፡፡ ነገርን ነገር ያነሳዋልና፣ የማንኩሳ ዘመዶቼ የሚያስደነግጥ ነገር ሲገጥማቸው ‹‹አቲቲን ወሰድከው›› ይላሉ፡፡ ቀልቤን ገፈፍከው ለማለት ነው፡፡ የኦሮሞ ባህላዊ ተጽእኖ በወለጋ ድንበር ላይ ቆሟል ያለው ማነው?

ስለጉዲፈቻ ባህል ብዙ ሰዉ የሚያውቅ ይመስለኛል፡፡ በጦርነት ወቅት ምርኮኞችን ባርያ ማድረግ ወይም መግደል በብዙ ማህበረሰቦች የተለመደ ነው፡፡ በኦሮሞ አበዋዊ ባህል ውስጥ ግን ምርኮኞች በልጅነት ይታቀፋሉ፡፡ ከሌላ ብሄረሰብ ቢመጡም የኦሮሞ ብሄረሰብ የሚያገኘውን መብት ሳይነፈጋቸው ያድጋሉ፡፡ ይህንን ልማድ በአማራው ማህበረሰብ ውስጥም እናገኘዋለን፡፡ ለምሳሌ በጎጃሙ ንጎስ ተክለይማኖትና በወለጋ መሳፍንት መሀል በተደረገው ጦርነት የተማረከው ብላቴና ነገሮ ዋቅጅራን እንደልጅ አሳድገውታል፡፡ ክርስትና አስነስተው ተክለኢየሱስ አሰኝተውታል፡፡ ራሱ በጻፈው ማስታወሻ ‹‹በጠጅና በስጋ አደግሁ›› በማለት የመሳፍንት ልጆች ያገኙት የነበረውን ምቾት ሳይነፈገው ማደጉን ይመሰክራል፡፡ ነገሮ ፣ ከማእረግ ወደ ማእረግ እየወጣ የንጉሱ ጸሐፌ ትዝዛዝ እስከመሆን ደርሷል፡፡ ተመሳሳይ መልኩ በሸዋ ምርኮኛው ቆሴ ዲነግዴ በቤተመንግስት እየተቀማጠለ አድጎ ሐብተጊዎርጊስ በሚል ስመ ክርስትና የኢትዮጵያ የጦር ምኒስትር እስከመሆን ደርሷል፡፡ ሰዎችን በልዩ ቋንቋቸው ምክንያት ባይተዋር ማድረግ ኢትዮጵያዊ ባህል አልነበረም፡፡

እኩዋን ባህላችን አማርኛችን እንኳ የጉራማይሌነታችን ምስክር ነው፡፡ አሁን ኦሮምኛ ያልተነካካ አማርኛ ማግኘት ይቻላል?፡፡ እሰቲ ለናሙና ያክል ‹‹ተወርዋሪ ኮከብ›› ከተባለው የዮሐንስ አድማሱ ምርጥ የአማርኛ ግጥም ውስጥ ጥቂት መስመሮች ልቆንጥር፡፡

1) ተወርዋሪ ኮከብ በራሱ ነበልባል በራሱ ነዲድ ተቃጥሎ የጠፋ
ተወርዋሪ ኮከብ በምናውቀው ሰማይ ነበረ በይፋ

2) ሜዳና ተራራ በመሐል ሸለቆ
ጨፌውና መስኩ በኒህ ተደብቆ

3) ሐቀኛ ጠፍቶበት በዋለበት መልቲ
ጌጥ ነው ድንቁርና የገዳዮች ሎቲ

4) ብልጭ ብሎ ጠፋ
ተወርዋሪ ኮከብ የሐሳብ አንጋፋ

በመረጥኳቸው መስመሮች ውስጥ የሚገኙት ‹‹ይፋ፣ ጨፌ፣ መልቲ፣ ሎቲ፣ አንጋፋ፣›› የተባሉት ቃላት ኦሮሚኛ ናቸው፡፡ ካንድ የአማርኛ ግጥም ይህን ያህል ኦሮሚኛ ከተገኘ በሙሉ መዝገበ ቃላት ውስጥ ምን ያህል ሊገኝ እንደሚችል አስቡት፡፡ ይህን ያክል ነው የተዋሀድነው፡፡

የኢትዮጵያ ባህል የተውጣጣ ባህል እንጂ ጃዋር እንደሚለው የአማራ ባህል ብቻ አለመሆኑን በመጠኑም ቢሆን ያሳየሁ ይመስለኛል፡፡ ጃዋርን እዚህ ላይ ላሰናብትና ለማጠናቀቂያ የምትሆን አንዲት አንቀጽ ልጨምር፡፡

ባህልን ማክበር ጥሩ ነው፡፡ ይሁን እንጂ በስሜት ሚነድደው የብሄርብሄረሰብ ፖለቲካችን፣ ዜጎች ለባህል ያላቸውን ፍቅር ወደ ጭፍን አምልኮአዊ ፍቅር እያዘቀጠው ነው፡፡

ባባቶቻችንና በእኛ መካከል የባህል ፋይዳ ልዩነት ያለ ይመስለኛል፡፡ አባቶች ባህላቸውን ያገኙት በኑሮ ጣጣ አስገዳጅነት ነው፡፡ ለምሳሌ የኔ አያት ቁምጣ ሱሪ የሚታጠቀው ከሌሎች ብሄረሰቦች ለየት ብሎ ለመታየት አይመሰለኝም፡፡ በቂ አቡጀዲ ስላላገኘ ነው፡፡ ወይም ለስራ እንዲያመቸው ባጭር መታጠቁ ይሆናል፡፡ እኔ ግን የብሄረሰቦች ቀን ሲከበር ቁምጣ ለብሼ ራሴን በማስጎብኘት እንድኮራ ይጠበቅብኛል፡፡ ጉድ እኮ ነው!!! ጋቢ በጥንት ጊዜ የሙቀት ምንጭ ነበር፡፡ ዘንድሮ የኩራት ምንጭ ሊሆን ይቃጣዋል፡፡

የዛሬዎቹ ባህል አምላኪዎች ባህል ሲያስቡ ለውጥን ይረሳሉ፡፡ ባንድ ወቅት የሚያኮራው ያንድ ብሄረሰብ ባህል በሌላው ወቅት ይናቃል፡፡ ባንድ ወቅት የሚያስሸልመው በሌላ ጊዜ ያስቀጣል፡፡ ከጥቂት መቶ አመት በፊት ዝሆን መግደል በማህበረሰቡ ዘንድ ትልቅ ከበሬታ የሚያጎናጽፍ ተግባር ነበር፡፡ ዝሆን የገደለ ልዩ አምባር ክንዱ ላይ ያጠልቃል፡፡ እስኪ ዛሬ ያባቶቼን ባህል ለማክበር ነው ብለህ ፓርክ ውስጥ አርፎ የተኛውን ዝሆን ግደል፡፡ በአምባር ምትክ ካቴና ይጠልቅልሀል፡፡

የብሄር ብሄረሰቦች አልባሳት የተባለውን የተደጋገመ ግን ያልታሰበበት ቃል ከዚህ አንጻር ቃኙት፡፡ ሲጀምር ፣ዛፍ እንኳ ቅርፊቱን በሚቀያይርበት ዓለም፣ብሄር ብሄረሰቦች በየጊዜው አልባሳታቸውን አይቀያይሩም ወይ?፡፡ የብሄረሰቡ አልባስ ሲባል በየትኛው ዘመን የሚለበሰው ነው? የእንዳለጌታ ከበደ እናት ሲነግሩን፣ ዛሬ በጉራጌ ዘፈን ላይ በቲቪ የምናየው የሴቶች ሻማ ቀሚስ በደርግ ዘመን የተጀመረ ነው፡፡ ከዚያ በፊት የነበረው ሸማ ነው፡፡ ከሸማው በፊት ደግሞ የቆዳ ቀሚስ ይለበስ ነበር፡፡

ሌላው፣ አንድ ማህበረሰብ አልባሳት በየማእረጉ ልዩ ልዩ ልብሶች ይኖሩታል፡፡ ወታደሩ ያባ ገዳውን ልብስ የሚለብስ አይመስለኝም፡፡ ባሮች ከጌቶች ልብስ ጋር የሚመሳሰል ልብስ እንዲለብሱ አይፈቀድላቸውም ነበር፡፡ በፊውዳል ማህበረሰብ ከላይ አስከታች መልበስ መከናነብ የጨዋነት ምልክት ነው፡፡ ይህንን በሸዋና በትግራይ ብቻ ሳይሆን በቅድመ ምኒልክ ከፋ ውስጥ እናገኘዋለን፡፡ ባንጻሩ፣ባሮች በከፊል ተራቁተው መታየት አለባቸው፡፡ ባጠቃላይ በኢትዮጵያ እስከቅርብ ጊዜ ድረስ አለባበስ በበሄረሰብ ላይ ሳይሆን በመደብ ላይ የተመሰረተ ሆኖ እናገኘዋለን፡፡ ስለዚህ የብሄር አልባሳት የሚባለው እንደ ማንኛውም ሾላ በድፍን ሐሳብ በጥርጣሬ መታየት አለበት፡፡

ትውልዱ የባህል ፈጣሪ መሆን ሲገባው፣የባህል ሙዚየም ሆኖ ተተክሏል፡፡አፈወርቅ ገብረኢየሱስ ባንድ ወቅት እንዳለው ‹‹ካባቶቹ የማይበልጥ ትውልድ፣ እንዳልተፈጠረ ይቆጠራል››

ማሳረጊያ

ኢትዮጵያን አንድ አድርጎ ያቆያት የነገስታቱ ጉልበት ብቻ ነው ብለው የሚያስቡ ሰዎች ኢትዮጵያ የተሸመነችበትን ውስብስብ ክር ማየት ያልታደሉ ናቸው፡፡ዛሬ ኢትዮጵያን በታትነን ክልላችንን እናድናለን ብለው ባደባባይ ሳያፍሩ የሚናገሩ ሰዎችን የምናይበት ዘመን ላይ ደርሰናል፡፡በርግጥ ኢትዮጵያ ማእበል ከበረታባት እንደ ታይታኒክ ትሰጥም ይሆናል፡፡ግን መርከቢቱ ስትሰጥም የመርከቢቱ ሳሎን ብቻውን አይንሳፈፍም፡፡የመርከቢቱ ጓዳ ብቻውን አይተርፍም፡፡ኢትዮጵያ ስትከስም ብሄሮች ተነጥለው ይለመልማሉ ማለት ተፈጥሮ አመሏን እንደ ግትቻ የትም ጥላለች ማለት ነው፡፡

Hiber Radio: በአቶ መለስ ልጅ ስም በኒዮርክ ባንክ አለ የተባለውን 5 ቢሊዮን ዶላር የሚያሳየው ቼክ ጉዳይ እንዲጣራ ለአሜሪካ መንግስት ሊቀርብ መሆኑ ተገለጸ

0
0

ጋዜጠኛ ሃብታሙ አሰፋ

ጋዜጠኛ ሃብታሙ አሰፋ

የህብር ሬዲዮ ዕሁድ ሐምሌ 21 ቀን 2005 ፕሮግራም

>

የግብጽን አብዮት በአብነት ከወቅታዊ ጉዳይ ጋር ቃኝተነዋል(ሙሉውን ያዳምጡት)

>አቶ ሞገስ ሽፈራው በቬጋስ በስራ ማቆም አድማ ላይ ያሉት አሽከርካሪዎች የሕግ ጉዳይ ኮሚቴ አባላት አንዱ

>

በተሳፋሪ የተደበደበ ኢትዮጵያዊ የታክሲ አሽከርካሪ በቬጋስ በዐይኑ አካባቢ በጉዳት እስከመሰፋት ስለደረሰበት ድብደባ ከተናገረው(ሙሉውን ያዳምጡ)

ሌሎችም ቃለ መጠይቆች አሉን

ዜናዎቻችን
በአቶ መለስ ልጅ ስም በኒዮርክ ባንክ አለ የተባለውን 5 ቢሊዮን ዶላር የሚያሳየው ቼክ ጉዳይ እንዲጣራ ለአሜሪካ መንግስት ሊቀርብ መሆኑ ተገለጸ

ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ የምርጫ 97ቱ ሚሊዮኖች የወጡበት የሚያዚያ 30 ሰልፍ በተግባር እንዲደገም ጥሪ አቀረበ

ግብጽ ኢትዮጵያ የህዳሴውን ግድብ እንድታቆም አስጠነቀቀች

ካይሮ ዛሬም በአመጽ እየተናጠች ነው

ጠበቃ ተማም የጸረ ሽብር ሕጉን ህገወጥነት በአንድነት ፓርቲ ሕዝባዊ ስብሰባ ላይ አስረዱ

የትራይቮን ማርቲን ገዳይ የሆነው ጆርጅ ዚመርማን ከሕግ ቢያመልጥ ከፈጣሪ ተጠያቂነት እንደማያመልጥ ከጉዳዩ ነጻ ካሉት ዳኞች አንዱዋ ተናገሩ

የሙስሊሙ ዓለም አቀፍ የተቃውሞ እንቅስቃሴ የተሳካ እንደነበር ተገለጸ

በቬጋስ የሚገኙ ሙስሊሞች ትግሉን ደግፈው በጋራ ተሰባስበው የአቋም መግለጫ አወጡ

ሌሎችም ዜናዎች አሉን

Sport: የአብራሞቪች 10 ዓመታት ቅኝት

0
0

(በዘ-ሐበሻ ጋዜጣ ቁጥር 53 ታትሞ የወጣ)

ሮማን አብራሞቪች ወደ ስታምፎርድ ብሪጅ ከመጡ 10 ዓመታት ተቆጠሩ፡፡ ራሺያዊው ቢሊየነር ቼልሲን በእጃቸው ካስገቡ ወዲህ ወደ ታላቅነት አሸጋግረውታል፡፡ ሰውዬው የእንግሊዝን እግርኳስም መቀየር ችለዋል፡፡ አብራሞቪች በቼልሲ ባለቤትነት ቆይታቸው የፈፀሟቸውን አብይ ኩነቶች እንመልከት፡፡

በእግርኳስ ፍቅር መውደቅ

በ2003 ነበር፡፡ በቻምፒየንስ ሊጉ ሪያል ማድሪድ በአስደናቂ መልኩ ማንቸስተር ዩናይትድን 4-3 ማሸነፍ ቻለ፡፡ በኦልድትራፎርድ ጨዋታውን ለመመልከት ከታደሙት መካከል ብዙም የማይታወቁ ራሺያዊ ቢሊየነር አንዱ ነበሩ፡፡ በምሽቱ ግጥሚያ በመመሰጣቸው ቀጣይ ጉዟቸው የእግርኳስ ክለብ መግዛት እንደሆነ ወሰኑ፡፡ ከበርቴው ጊዜያቸውን ሳያጠፉ ቼልሲን የግላቸው አደረጉ፡፡
ቼልሲ በለንደን የሚገኝ መሆኑና የአክሲዮን መዋቅሩ ክለቡን በቀላሉ እንዲያገኙት አድርጓቸዋል፡፡ ክለቡን ለመግዛት በአብራሞቪችና በወቅቱ የቼልሲ ቺፍ ኤግዚኪዩቲቭ ትሬቨር ቢርች መካከል ውይይት ተደረገ፡፡ ‹‹አብራሞቪች ክለቡ ሊገዛ መፈለጉን ሙሉ ለሙሉ ለማመን ተቸግሬ ነበር›› ይላል ቢርች፡፡ አብራሞቪች ክለቡን ለመጠቅለል የተጠየቁትን ገንዘብ ለመክፈል ተስማሙ፡፡ ከቢርች ጋር ያደረጉት ድርድርም 20 ደቂቃ ብቻ የፈጀ ነበር፡፡ ቢርች በወቅቱ የቼልሲ ባለቤት የነበሩት ኬን ቤትስን ካነጋገሩ በኋላ በቀጣዩ ቀን በዶርቼስተር ሆቴል ለመገናኘት ቀጠሮ ያዙ፡፡ አብራሞቪች ቼልሲን ለመግዛት 140 ሚሊዮን ለመክፈልና እዳውን ለመሸፈን በመስማማት ድርድሩ ተቋጨ፡፡ ከዚያም ሮማን በሁለት ወራት ውስጥ ለተጨዋቾች ግዢ ከ100 ሚሊዮን ፓውንድ በላይ አውጥተዋል፡፡ በሁለት ዓመታት ጊዜ ደግሞ ጆን ቴሪ የፕሪሚየር ሊጉን ዋንጫ ከፍ አድርጎ ማንሳት ችሏል፡፡ የእንግሊዝ እግርኳስም በለውጥ ጎዳና መጓዙን ጀመረ፡፡
chealsea
አሽሊ ኮል ውዝግ
አቭራሞቪች ያለገደብ ገንዘባቸውን እንደሚያፈሱ ግልፅ የሆነው ወዲያው ነበር፡፡ በገንዘብ ጡንቻቸው የሚፈልጉትን መግዛት እንደሚችሉ አሳዩ፡፡ የወቅቱ የማንቸስተር ዩናይትድ ቺፍ ኤግዚኪዩቲቭ ፒተር ኬንየንን ወደ ስታምፎርድ ብሪጅ በማምጣት ሽግግሩን በፍጥነት መከወን ጀምረዋል፡፡ አብራሞቪች ካግሊያሪን ለመግዛት ሙከራ አድርገው እንደነበርም ተዘግቧል፡፡ ለዚህ ምክንያታቸው የሰማያዊዎቹ ኮከብ የነበረው ጂያን ፍራኮ ዞላ የጣልያንን ክለብ ለመቀላቀል በመፈለጉ ተጨዋቹን በስታምፎርድ ብሪጅ ለማቆየት ሲሉ ነበር፡፡
የቼልሲው ባለቤት በወቅቱ በግዢ ሪከርድነት ሊያዝ የሚችል 50 ሚሊዮን ፓውንድ ለአርሰናል በማቅረብ ቲዮሪ ሆንሪን ለማስፈረም ሞክረው ነበር፡፡ ሮማን ዕድሜው ለገፋው አንድሬ ሼቭቼንኮ ግዢ 30 ሚሊዮን ፓውንድ ማውጣታቸው ስህተት ከፈፀሙባቸው ዝውውሮች አንዱ ሆኗል፡፡ የሚፈልጓቸውን ተጨዋቾች ለማምጣት አብራሞቪች እጃቸውን ወደ ኪሳቸው ከማስገባት ወደኋላ አይሉም፡፡
ቼልሲ የትኛውንም ተጨዋች ለማስፈረም ከአቅሙ በላይ እንደማይሆን ማመን ጀመረ፡፡ ለተጫዋች ዝውውር ከፍተኛ ሂሳብ ለመክፈል ፍቃደኛ መሆኑ በበርካቶች ዘንድ አነጋጋሪ ሆነ፡፡ የአሽሊ ኮል ዝውውር ውዝግብ በጥሩ ምሳሌነት ይጠቀሳል፡፡ ጆዜ ሞውሪንሆ ከአርሰናሉ የግራ መስመር ተጨዋች ጋር በለንደን አንድ ሬስቶራንት በመገናኘት በመወያየታቸው ቼልሲ ያለ አርሰናል ፍቃድ ኮልን በማነጋገሩ ጥፋተኛ ተብሎ ነበር፡፡ አርሰን ቬንገርም በወቅቱ የቼልሲን አቀራረብ ህገወጥ የፋይናንስ ስራ ብለውት ነበር፡፡ በመጨረሻ አብራሞቪች የሚፈልጉትን ተጨዋች አግኝተዋል፡፡ ኮል ወደ ቼልሲ ከመጣ ወዲህ ክለቡ ስምንት ታላላቅ ዋንጫዎችን ማሸነፍ ችሏል፡፡

አዲስ የልምምድ ማዕከል
የአብራሞቪች ረብጣ በተጨዋቾች ዝውውር ላይ ብቻ አልፈሰሰም፡፡ በቼልሲ ለረጅም ጊዜ የሚዘልቅ መሰረተ ልማት በማካሄድ ላይም ውሏል፡፡ በአሁኑ ወቅት ቼልሲ በፋይናንስ አቅሙ በዓለም ላይ ከሚገኙ ታላላቅ ክለቦች ጎራ የሚቀላቀልበት ደረጃ ላይ ይገኛል፡፡ በቅርቡ ዴሎይቴ ባወጣው መረጃ ቼልሲ አርሰናል፣ ኤሲሚላን፣ ሊቨርፑልና ጁቬንቱስን በመብለጥ ከዓለም ታላላቅ ክለቦች ዝርዝር ላይ በአምስተኛነት ተቀምጧል፡፡ በአብራሞቪች ዘመን ለመጀመሪያ ጊዜ ክለቡ ትርፍ አስመዝግቧል፡፡ ከ700 ሚሊዮን ፓውንድ በላይ የሆነው ብድር ወደ ወለድ የማይከፈልበት ብድር ተሸጋግሯል፡፡ ክለቡ አሁን ከእዳ ነፃ ነኝ ሊል ይችላል፡፡
ሮማን ቼልሲን በሁሉም ዘርፍ በፍጥነት እንዲያድግ ያደረጉት ጥረት በግልፅ ይንፀባረቃል፡፡ ከሀርሊንግተን የልምምድ ማዕከል በ2007 ወደ ተከፈተው ኮብሃም መዛወር ችለዋል፡፡ አብራሞቪች በወጣት አካዳሚው ላይ ያፈሰሱት ገንዘብ አሰልጣኞች ለወጣቶች እድል ለመስጠት በቂ ጊዜ ስለማያገኙ ስኬታማ ለመሆን አልቻለም፡፡ ቼልሲ ወጣቶችን እንዲያፈራ ያላቸው ፅኑ ፍላጎት ግን አነስተኛ ግምት የሚሰጠው አይደለም፡፡

የአቭራም ግራንት ሹመት
አብራሞቪች በቼልሲ በቆዩባቸው ያለፉት 10 ዓመታት ከፈፀሟቸው ተግባራት የሚጎላው የአሰልጣኞች ሹም ሽራቸው ነው፡፡ ጆዜ ሞውሪንሆን እንዲያሰናብቷቸው የገፋፋቸው በኮሪደር ላይ ፖርቹጋላዊው ሊያብራሯቸው እንደማይችሉ በመግለፃቸው ምክንያት እንደሆነ ዘገባዎች ይጠቁማሉ፡፡ በእርግጥ ሮማን ቁልፍ በሆኑ አማካሪዎቻቸው ያልተቋረጠ ድጋፍ ያገኛሉ፡፡ ከሊቀመንበሩ ብሩስ ባክ እስከ ዳይሬክተሮቹ ዩጂን ቴኔንባውምና ማሪና ግራኖቭስካይ ድረስ በዙሪያቸው አሉ፡፡ በባለሀብቱ ወሳኝ ሰዎች ተርታ በተለያዩ ጊዜ የገቡ ሌሎች ሰዎችም አሉ፡፡
ከእነዚህ መካከል የራሺያዊው ጥሩ የሆኑት አብራም ግራንት ይጠቀሳሉ፡፡ ግሪ በእስራኤል የሰሩት ስራ በቼልሲ የፉትቦል ዳይሬክተር መሆን እንደሚያስችላቸው አብራሞቪችን በማሳመን በ2007 ኃላፊነቱን ተረከቡ፡፡ በኋላም ጆን በመተካት የአሰልጣኝነቱን ወንበር ተቆናጠጡ፡፡ ግራንት ቼልሲን በቻምፒየንስ ሊጉ ፍፃሜ ቢያደርሱትም በማንቸስተር ዩናይትድ ተረትተው ዋንጫውን ሳያነሱ ቀሩ፡፡ የግራንት ስኬታማ ጉዞ አሰልጣኝ መቀያየር ውጤት እንደማይኖረው ለሮማን የቀረበ ማስረጃ ነበር፡፡ በኋላም አብራሞቪ ሉዊዝ ፌሊፔ ስኮላሪ፣ ጉስ ሂዲንክ፣ ካሮል አንቼሎቲ፣ አንድሬ ቪያስ-ቦአስ፣ ሮቤርቶ ዲ ማቲዎ እና ራፋ ቤኒቴዝን ቀያይረዋል፡፡ ወቅቱ የተጨዋቾች ተሰሚነት ይበልጥ የጎለበተ ነበር፡፡ ‹‹የአሰልጣኝነት እድሉን ለመጠቀም ካሰብክ ምናልባት ራስህን መጀመሪያ ማሰናበት አለበህ›› በማለት ፍራንክ ላምፓርድ ስለሚፋጀው ወንበር ተናግሮ ነበር፡፡

ከሙኒኩ ድል በኋላ ያደረጉት ንግግር
ባለፉት 10 ዓመታት አብራሞቪች ለእግርኳሱ ያላቸው ፍቅር በመቀዝቀዙ ቼልሲን የሚገዛ ባለሀብት ሊፈልጉ እንደሚችሉ ጭምጭምታዎች ይሰሙ ነበር፡፡ አብራሞቪች በዝውውር ላይ ገንዘባቸውን የቆጠቡበት ጊዜ ነበር፡፡ በስታዲየም ተገኝተው የታደሙበት ጨዋታዎች ብዛት አነስተኛ የነበረበት ወቅትም ነበር፡፡ በአንድ ወቅት ትኩረታቸውን ከቼልሲ ውጪ አድርገውም ነበር፡፡ ከራሺያዊው ጎን ያሉ ሰዎች ግን ባለሀብቱ ለእግርኳስ ያላቸው ፍቅር አለመቀዝቀዙን እና ለቼልሲ የሰነቁት ራዕይ እንደ ቀድሞው ጠንካራ መሆኑን በተደጋጋሚ ይገልፁ ነበር፡፡
ቼልሲ በ2011/12 ቻምፒየንስ ሊጉን ካሸነፈ በኋላ በመልበሻ ክፍል አብራሞቪች ያደረጉትን ንግግር ያደመጡ ሰውየው ስለወደፊቱ እያሰቡ እንደሆነ ገልፀዋል፡፡ ‹‹ሮማ በመልበሻ ክፍሉ አጭር የምስጋና ንግግር አድርገዋል›› ሲሉ ባክ በወቅቱ የተከሰተውን ተናግረው ነበር፡፡ አብራሞቪች በቴኔንባውም አስተርጓሚነት በተረጋጋ መንፈስ ‹‹አሸንፈናል፡፡ ይህ ግን ገና መጀመሪያችን ነው›› ብለዋል፡፡

ጋርዲዮላ ሲያጡ ፊታቸውን ወደ ሞውሪንሆ መልሰዋል
ዲ ማቲዎ የቻምፒየንስ ሊጉን ዋንጫ ካመጣ ከስድስት ወራት በኋላ ከኃላፊነቱ ሲነሳ ዎል ስትሪት ጆርናል ‹‹የቼልሲ አሰልጣኝ ለመሆን የሚፈልግ ማነው?›› የሚል ርዕስ አውጥቶ ነበር፡፡ በእርግጥ መልሱ በርካታ ሰዎች የሚል ቢሆንም ርዕሱ የአብራሞቪችን አካሄድ በጥሩ ሁኔታ ይገልፃል፡፡ ሮማን አሰልጣኞችን የሚያሰናብቱት ዋንጫዎች ብቻ ፈልገው ሳይሆን ማራ አጨዋወት መመልከት ስለሚፈልጉም ጭምር ነው፡፡ ነገር ግን በርካታ አሰልጣኞችን መቀያየራቸው አማራጫቸውን ገድቦባቸዋል፡፡
ፔፕ ጋርዲዮላ ከቼልሲ ይልቅ ባየር ሙኒክን የመረጠው የተሻለ ገንዘብ ፍለጋ አለመሆኑ ግልፅ ነው፡፡ ስፔናዊውን ያጡት አብራሞቪች አማራጭ ስለሌላቸው ሞውሪንሆን በድጋሚ ለማስፈረም ተገደዱ፡፡ የጆዜ ቅጥር በአሰልጣኞች ላይ ያሳለፏቸው ውሳኔዎች ስህተት እንደነበሩ የመቀበል አይነት ይመስላል፡፡ ምናልባት ስኬታማ የነበሩት ሞውሪንሆን ማሰናበታቸው ስህተት እንደነበር ያመኑበት ሊሆን ይችላል፡፡ አሰልጣኞች ቢቀያየሩም ክለቡ ዋንጫዎቹን ማሸነፍ ችሏል፡፡ ሞውሪንሆን ባለፉት 10 ዓመታት በቼልሲ ቆይተው ቢሆን ቡድኑ ምን ያህል ዋንጫዎችን ሊያሸንፍ ይችል ነበር? የሚለው ጥያቄ ይነሳል፡፡ አብራሞቪችና ሞውሪንሆ ለረጅም ጊዜ የሚዘልቅ መረጋጋት እንደሚመርጡ እየተዘገበ ይገኛል፡፡ ከዚህ ውጪ በክለቡ ያለው ፍላጎት ማሸነፍ በቻ ሳይሆን በማራኪ አጨዋወት ስኬታማ መሆንም ጭምር ነው፡፡


አስከፊው ስርዓት ከውስጥም ከውጭም ተወጥሯል።

0
0

አበራ ሽፈራዉ/ከጀርመን/

አበራ ሽፈራዉ /ከጀርመን/

አበራ ሽፈራዉ /ከጀርመን/

የኢትዬጵያን ሕዝብ ሰብአዊና ቁሳዊ መብቶች በነፆነት ትግል ሰበብ ሕወሐት ለአለፉት 39 ዓመታት ሲረግጥ ቆይቷል።በመግቢያዬ ላይ ሀሳቤን በዚህ መልክ እንዳጠቃልል ያደረገኝ ደግሞ ባለፉት 39 ዓመታት የተከናወኑትን መለስ ብዬ ሳያቸው ከሰመሗቸው፣ካየሗቸውና ካነበብኳቸዉ እንደተረዳሁት በእርግጥም  ኢትዬጵያውያን በነዚህ ዓመታት በሕወሐት የለየለትና መሰሪ ተግባር  የተነሳ ሲገደሉ፣ሲታሰሩ፣ሰብዓዊ መብታችን ሲረገጥና፤በነፆነት ሥም ብዙዎች በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ለሕወሐት ጥቅም አስፈፃሚነት ሲሞቱ አልያም የጥቅሙ ተቀናቃኞች በሙሉ ሕይወታቸዉን ሲያጡ ቆይተዋል፤አለፍም ካለ ደግሞ ያፈሩትን ንብረትና ሀብትም ለማጣት ተገደዋል፣ተዘርፈዋል፣ ተነጥቀዋል ፤እምቢ ካሉም ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ከዚህ አለም በጥይት ተገድለው በሞት ተለይተዋል ።

ከደርግ መንግስት ዉድቀት በኋላም ለ22 ዓመታት የታየው ተጨባጭ ሁኔታ በርግጥም እነዚህ ሕወሐቶች የኢትዬጵያ ቀንደኛ ጠላቶች መሆናቸውን አለምንም እፍረትና ይሉኝታ ሲያቅዱና ሲተገብሩ ቆይተዋል፤አሁንም ቀጥለዋል፤ተዉ ያለም የሚጠብቀው እስር፣ግርፋት፣መሰደድና ሞት መሆኑ ለሁሉም ኢትዬጵያውያን ብቻ ሳይሆን ዓለም እያወቀው ያለ ጒዳይ ሆኗል።

የውጭ ሀገራት የዲኘሎማሲና የውጭ ግንኙነቱም በተወሰኑ የጥቅም ግንኙነት ላይ ብቻ ባተኮረና የኢትዬጵያን ሕዝብ ጥቅም ወደጐን በተወ መልኩ የተከናወነ ሆኖ ቆይቷል፤በውጭ ሀገራት የዲኘሎማሲ ማህበረሰብ የሠብአዊና የፍትሕ ጥያቄ ሲቀርብ ግን እርሱ የእኔ ጒዳይ ነው ተዉት እያለ የሰው ልጆችን ከሰብዓዊነት ውጭ በመጨቆን በዚህ ዘመን የማይጠበቅ የጭቆናና የብዝበዛ ስርዓት በመሆን ቀጥሏል፤በየትኛውም የዓለም ሀገራት የማይፈፀም ግፍ ዛሬ በኢትዬጵያ ይፈፀማል።

የኢትዬጵያ ሕዝብ የሚያታግለው ስለአጣ ብቻ ሳይሆን ለዘመናት ያካበተው ርህሩሕነት፣ቸርነት፣ቻይነት፣ይቅር ባይነት፣በመቻቻል አብሮ በጋራ መኖርንና መስማማትን ይዞ የኖረ ሕዝብ በመሆኑ ዛሬ ሕወሐት/ኢሕሐዴግ እነዚህን ጠቃሚ የማህበራዊ አኗኗር እሴቶች ለመጣል እየሞከረ ይገኛል፤ይሁንና በሕዝቡ ላይ ከልክ ያለፈ ግፍ በመፈፀሙና እነዚህን ለአገሪቷም ሆነ ለመሪዎቿ የሚጠቅሙ የማህበራዊ አኗኗር እሴቶችን ከሕዝቡ ላይ ለመሸርሸር በመሞከሩ ዛሬ ሕወሐት/ኢሕሐዴግን ለመጋፈጥ ብዙዎች ወደ ትግሉ እየተቀላቀሉ ይገኛሉ።

ሕወሐት/ኢሕሐዴግ ከለየለት ጥፋቱ ለመመለስ ባለመፈለጉና የሕዝብን ትግስት እንደፈሪ በመቁጠሩ ዛሬ ውጥረቱ

በራሱ በሕወሐት/ኢሕሐዴግ ላይ ነግሷል፤ ወደደም ጠላም ተወጥሯል፤ሕዝቡ በድፍረት በሠላማዊ ሠልፍ ብቻ ለሕወሐት/ኢሕሐዴግ ጥላቻዉን እየገለፀ ይገኛል፤ይህም በሕወሐት/ኢሕሐዴግ ሠፈር ትልቅ ድንጋጤን በመፍጠሩ የዉጥረቱን መጠን ለመቀነስ የሚደረጒ ልዩልዩ ስብሰባዎችም ቢሆኑ ሌላ ተጨማሪ ድንጋጤን በገዢዎቻችን ሠፈር እየፈጠሩ ይገኛሉ።

ሕወሐት/ኢሕሐዴግ የዲሞክራሲና የፍትህ ፅንሰ ሐሳቦች በፍፁም የማይገባዉና በ60ዎቹ የሶሻሊስት አስተሳሰቦች ተተብትቦ ፤በሰብአዊ ፍጥረት ላይ ባለዉ ንቀት የተነሳና ይኸዉ አሮጌ አስተሳሰቡ ዓለም ካለችበት ተጨባጭ ሁኔታ ጋር አብረዉ ሊጓዙ የሚችሉ ወጣቶችን ለመሰብሰብ ባለመቻሉ፣የአስተሳሰብ ለውጥ ለማምጣት ባለመፈለጉና በዚሁ አሮጌ አስተሳሰቦችና በጥላቻ ፖለቲካ በተመረዙ ሰዎች እየተመራ በመሆኑ ዛሬ ውጥረቱ በራሱ በድርጅቱ ዉስጥ እየሰፋ መምጣቱን ከራሱ ከድርጅቱ የሚወጡ መረጃዎች ያሳያሉ።

ዛሬ ኢትዬጵያ ግልፅ ባልሆነ መልኩ በተደራጁ ማፍያዎች እንደምትመራ ኢትዬጵያን ብቻ ሳይሆኑ የአለም መሪዎች ጭምር እያወቁ የመጡ ይመስላል።

በቅርቡ እንኳን በዩናይትድ ስቴት ኦፍ አሜሪካ በጁን 20,2013 በኮንግረስ ማን የተከበሩ ስሚዝ ሰብሳቢነት በኢትዩጵያ ባለው የሰብአዊ መብት አያያዝ ላይ ከመለስ በኋላ የምስክርነት ቃል መስማት በተከናወነበት ወቅት የተሰነዘሩት አስተየቶችና ለኢትዬጵያ መሪዎች ማነቆ የሚሆኑ ሕጐችን ለማውጣት ቃል መግባታቸዉን ስንመለከት አሜሪካ ከዚህ ስብሰባ በስተጀርባ በኢትዩጵያ ጉዳይ ላይ ያላትን ዕቅድ ለመተግበር መነሳቷን አልያም የሕወሐት/ኢሕሐዴግ መሪዎች አካሄድ እንዳላስደሰታቸው ያመለክታል።

 

ባለፈው ሰሞን የኢትዩጵያ የልማት ድጋፍ ስጪ አገሮች አምባሳደሮች የሰማያዊ ፖርቲ አመራርን ለማነጋገርና አንዳንድ መረጃ ለመለዋወጥ ማቀዳቸውና መተግበራቸው ከሕወሐት/ኢሕሐዴግ የይስሙላ ዴሞክራሲ ጋር ቅራኔ አንዳላቸውና በሕዝብ እንቅስቃሴም ዙሪያ የተለየ እይታ ይዘው መቅረባቸውን ፤እንዲሁም ለዘለቄታ ግንኙነታቸውና ጥቅሞቻቸው ሕዝብ ከጠላው ጋር መስራታቸው በታሪክ ሊያስጠይቃቸው እንደሚችል የገባቸውና ፤እነሱም ለውጥ ፈላጊ መሆናቸውን ማየት ይቻላል።

 

አውሮፓ ሕብረት የፖርላማ ተወካዬች በሰብአዊ መብት አያያዝ ዙሪያ ለመነጋገር በኢትዩጵያ ያደረጉትን ጉብኝት ብንመለከት ደግሞ «ኑና እዪ»  የተባሉ ይመስል ሕዝቡ ላይ ያለዉን ችግር እራሳቸው በቅርበት ያዩትና እራሳቸውን ጭምር ያሳዘናቸው መሆኑና ፤የኢትዩጵያ ችግር እምን ደረጃ እንደደረሰ ለመረዳት ችለዋል። እነዚህ የአውሮፓ ህብረት የፖርላማ አባላት ኢትዩጵያ በምን አይነት ሰዎች እንደምትመራ ለመረዳት እንደቻሉና የተለየ አግራሞት እንደፈጠረባቸዉ በቀላሉ መረዳት ይቻላል ፤ ከዚህም የተነሳ ይመስላል የህብረቱ አባላት የታሰሩ ጋዜጠኞችና የተቀዋሚ ፖለቲካ ፓርቲ አባላት ከስር እነዲለቀቁ ፣ሀሳብን በነፃነት የመግለጽ መብት እንዲከበር ፣የእምነትና የሀይማኖት ተቋማት መብትና ነፆነት እንዲከበር መግለጫ እስከማዉጣት የተገደዱት።

 

ይህ ብቻ አይደለም በሃገራችን በሁለቱ ትልልቅ የሐይማኖት ተቋማት አካባቢ ያለዉ « የፍትህ ያለህ » ጥያቄዎች በኢትዩጵያ መሪዎች ጆሮ ዳባ ልበስ ባይነት ችግሩ እየተባባሰ ለመፍታት ወደሚቸግር አቅጣጫ እየመጡ መሆኑ የየዕለት ዜናዎች ሆነዋል።

 

ሌላው የሕወሐት/ኢሕሐዴግ ባለስልጣናት በመላው ዓለም ከኢትዩጵያን ጋር በልዩ ልዩ ጉዳዮች ላይ ለመነጋገር በሚንቀሳቀሱበት ጊዜ የሚገጥማቸዉ ተቃዉሞ በሌሎች  አገሮች ህዝቦች የሌለ በመሆኑ ህወሃቶች ምን ያህል በአገራቸዉ ዜጎች ዘንድ የተኮንኑ ለመሆናቸዉና አመኔታ የማይጥልባቸው መሆኑ እየታወቀ መምጣቱና በኢትዩጵያ አስክፊዉ ስርአት መሪዎች አካባቢ ትልቅ ድንገጤን እየፈጠረ መምጣቱ የቅርብ ጊዜያት እዉነታዎች ናቸዉ።

 

በቅርብ ደግሞ በሶስቱ ዋናዋና በአገር ውስጥ የስላማዊ ትግል አራማጅ ፓርቲዎች ማለትም በሰማያዊ ፓርቲ፣በአንድነትና በመድረክ ላይ እየደረሰ ያለው የስም ማጥፋት ዘመቻ በህዝቡ ተቀባይነት ባይኖርዉም እንደለመደዉ ለጥቃት መዘጋጀቱንና በነዚህም ፓርቲዎች አባላተ ላይ እየደረሰ ያለዉ እስራትና ማዋከብ በሕወሐት/ኢሕሐዴግ ፓርቲ ላይ ትልቅ ውጥረትና ድንጋጤ መፍጠሩን ያመለክታል።

 

ሌላው በተለያዩ ጊዜያት ሕወሐት/ኢሕሐዴግ ለኤርትራ መንግስት የሚያቀርባችዉ በስጦታ የታጀቡ የንታረቅ ልምምጦች  ድንገት ሊነሳ የሚችል ጦርነት በስልጠናቸው ላይ የሚፈጥረዉ ችግር ትልቅ ፍርሃት እንደፈጠረባችውና ለስልጠናቸዉ ሲሉ የትኛውንም ነገር ለመስጠት መዘጋጀታቸዉን ያሳያል።

 

እነዚህ በገዢዉ ፓርቲ አካባቢ ያሉት ዉጥረቶች በስለላ መዋቅር ብዛት ፣ በስር ቤቶች ብዛት ፣ በወታደራዊ ትጥቅና ስልጠና ብዛት መፍትሄ  የማያገኙባቸዉ ዋናዋና ምክንያቶች ህዝቡ ክልክ ያለፈ ጭቆና ዉስጥ መዉደቁ ፣ግልጽ ዘር መድሎ መኖሩ፣ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት በሙስና መዘፈቃቸዉና የገዢዉ ፓርቲ ንግድ ተቋማት የንግድ ብዝበዛና ሌሎችም ህዝቡን ስላስመረረዉ ትግሉ የማይቆም ትግል መሆኑን ሁሉም ኢትዮዽያዊ እየተረዳ ያለው ሀቅ መሆኑም ጭምር ነው።

 

በአለፉት ዓመታት በዝርፊያ ፣በዘር ማጥፋት ተግባር ፣ ህዝቡን በማሰርና በመግደል፣በዘረኝነት መድሎ፣ በከፍተኛ ሙስና ተግባርና በሌሎችም ሀገርንና ህዝብን ሊጎዱ በሚችሉ ተግባራት ላይ መሰማራቱ ሊቀጥል እንደማይችል ሁሉም የተረዳዉ ሀቅ ሆኗል ።

 

ተቃዋሚ ፓርቲዎች የስቪክ ማህበራትና ሌሎች የሀገሬ ጉዳይ ያገባኛል የሚሉ ሁሉ አሁን ኢትዩጵያ ካለችበት ሁኔታ አንፃር  ኢትዩጵያን ከለየለት ጭቆና ለማላቀቅ በሚደርገዉ ትግል ይበልጥ መስባስብ ፣መመካከርና የመፍትሄ አቅጣጫን አስቀምጦ መንቀሳቀስ ጊዜዉ የሚጠይቀዉ ጉዳይ በመሆኑና የሕወሐት/ኢሕሐዴግ ውጥረት በህዝቡና በሃገሪቷ ላይ ሌላ ተጨማሪ ችግር እንዳይፈጥር አስቀድሞ መከላከል ጠቃሚ ነው እላለሁ።

 

እግዚአብሔር ኢትዩጵያን ይባርክ!

በጀርመን በተለያየ ከተማ የሚገኙ የEPCOU አባላት የአንድነት ፓርቲ ያወጣውን የሚሊዮኖች ድምጽ ለነጻነት ተግባራዊ ይሆን ዘንድ የትብብር እንቅስቃሴ ጀምረዋል

0
0
 German2
እኛ በጀርመን ሀገር የምንገኝ ኢትዮጵያውያን በዜግነታችን በመሰባሰብ የወያኔን አምባገነን ስርአት አቅማችን በፈቀደው ሁሉ በማጋለጥ ላይ እንገኛለን  እናንተም ይህ ስራችን በተደጋጋሚ በድህረ ገጻቹ ላይ በማስቀመጥ ከፍተኛ ድጋፍ ሰታችሁናል ለዚህም ከፍተኛ ምስጋና እያቀረብን አሁንም በተመሳሳይ በሀገር ውስጥ የሚታገሉ ሰማያዊ ፓርቲና የአንድነት ፓርቲ የሚያደርጉትን እንቅስቃሴ በመደገፍና በዚሁ አጋጣሚ የወያኔን አምባገነን ስርአት ለማጋለጥ በጀርመን ከተሞች የተለያዩ ዝግጅቶችን በማደረግ ህዝባዊ ድጋፋችንን ለማደረ  እንቅስቃሴ ጀመረናል ስለዚህ ይህንን ስራችንን ለሎች ወገኖቻችን ያውቁት ዘንድ በድህረ ገጻቹ ላይ በማስቀመጥ እንድትተባበሩን ወገናዊ ትብብራችሁን እየጠየቅን በሁለተ ከተማዎች ላይ ያደረግናቸውን እንቅስቃሴዎች የሚያሳይ ሪፖርት የላክንላችሁ መሆኑን እየተቆምን ወደፊትም በተከታታይ የምንልክ መሆናችንና ትብብራቹ እንዳይለየን በአደራም ጭምር ነው …...ቀጣዩን ለማንበብ እዚህ ይጫኑ

የጅንካ ሕዝብ በአድማ በታኝ ፖሊሶች ታጅቦ ሰልፉን በሰላም አጠናቀቀ፣ አርባ ምንጭና ወላይታ ላይም ሕዝቡ ድምጹን አሰማ

0
0

(ዘ-ሐበሻ) “የሚሊዮኖች ነፃነት በኢትዮጵያ” በሚል አንድነት ፓርቲ በተለያዩ ከተሞች ከጠራው ህዝባዊ ስብሰባ እና የተቃውሞ ሰልፍ አካል አንዱ የሆነውና በጅንካ ከተማ የተካሄደው የተቃውሞ ሰልፍ በሺዎች የሚቆጠሩ የጂንካ ነዋሪዎች ሲወጡ በአድማ በታኝ ፖሊሶች የቅርብ ክትትል እንደነበር ከስፍራው ያገኘነው መረጃ አመለከተ።
ምንም እንኳ ህዝቡ ላይ ሽብር ለመንዛትና እንዳይወጣ ለማስፈራራትም ጭምር ነው የአድማ በታኙ ብዛት የታየው የሚሉ አስተያየት ሰጪዎች ቢኖሩም የጅንካ ህዝብ ግን በተቃውሞ ሰልፉ ላይ በመውጣት የተገፈፈው መብቱ እንዲከበር ጠይቆ በሰላም አጠናቋል ተብሏል።
አንድነት ፓርቲ በጅንካ ከተማ የዛሬው ተቃውሞ ከመደረጉ በፊት እንዳይቀሰቅስና ሰልፉም እንዳይካሄድ በመንግስት ከፍተኛ ጫና እየተደረገበት መሆኑን ሲግልጽ የነበረ ሲሆን ይህ ጫና ሰልፉ በሰላም እሰከሚጠናቀቅ ድረስ መቆየቱ ተዘግቧል።
ከጅንካ በተጨማሪም በአርባ ምንጭ አንድነት የጠራው የተቃውሞ ሰልፍ እንዲሁ ዛሬ ሲካሄድ ውሏል። በአርባምንጭም እንዲሁ በሺዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን ይህን ሰልፍ ታድመውታል።
በሌላ በኩልም በወላይታ አንድንት የጠራው ሕዝባዊ ስብሰባ በሰላም ተጠናቋል። አንድነት እንደገለጸው “ስብሰባውን የከፈቱት የአንድነት አመራር ይህን ሁሉ አፈና እና ማስፈራራት ተቋቁሞ በአዳራሹ የተገኘውን ህዝብ “ጀግኖች ናችሁ” ሲሉ አወድሰዋል። ወ/ሮ ሀድያ የሚባሉ የአንድነት አመራር አባል በቅስቀሳ ወቅት ተይዘው እንደታሰሩና አሁንም በእስር ላይ እንደሚገኙ ስብሰባውን የሚመሩት የአንድነት አመራሮች ለህዝቡ ይፋ አድርገዋል።”

በጅንካ፣ በአርባምንጭና በወላይታ ስለተደረጉት ሕዝባዊ እንስቃሴዎች ተጨማሪ መረጃዎች እንደደረሱን እንመለሳለን። እስከዚያው በጅንካ እና በአርባ ምንጭ የተሰሙት መፈክሮችን በከፊል እነሆ፦

• የታሰሩ የፖለቲካ እና የህሊና እስረኞች ይፈቱ
• መንግስት ህገ-መንግስቱን ያክብር
• መንግስት በኃይማኖት ጉዳይ ጣልቃ መግባቱን ያቁም!
• መንግስት ለብሄራዊ መግባባት ባስቸኳይ መልስ ይስጥ!
• ውሸት ሰልችቶናል! ይቁም!!!
• የጸረ – ሽብር ህጉ ባስቸኳይ ይሰረዝ!
• ዘርን መሰረት ያደረገ ማፈናቀል ባስቸኳይ ይቁም!!
• ሙወስና የስርአቱ መገለጫ ነው!!
• የአባይ ጉዳይ የኢትጵያ ሕዝብ ነው!
• ለተከሰተው የኑሮ ውድነት ተጠያቂው መንግስት ነው!!
• የዜጎች ሰብአዊ መብታቸውን የማግኘት መብታቸው ይከበር!!
• ዜጎች በሀገራቸው ስራ የማግኘት መብታቸው ይከበር!!
• በአባይ ጉዳይ ወሳኙ የኢትጵያ ሕዝብ እንጂ ግብጾች ይደሉም!!
• የፓርቲ አባልነት በፍላጎት መሆን አለበት!!
• ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ

በሚኒያፖሊስ 9 የኢትዮጵያውያን ንግድ ቤቶች በቃጠሎ ወደሙ

0
0

(ዘ-ሐበሻ) በሚኒያፖሊስ ሚኒሶታ 9 የኢትዮጵያውያን የንግድ ቤቶችን ጨምሮ የሌሎች ንግድ ቤቶችን የያዘ ሕንጻ በቃጠሎ ወደመ። ጁላይ 31 ቀን 2013 ዓ.ም ከምሽቱ 11:40 ላይ በተነሳው በዚህ ቃጠሎ የኢትዮጵያውያን ጋራዦች፣ የግሮሰሪ ሱቅ እንዲሁም የሕፃናት ደይ ኬር (ሕፃናት መዋያ) ሙሉ በሙሉ በቃጠሎ መውደማቸው ታውቋል።

በቃጠሎው የወደመው ሳብሪና ግሮሰሪ (ፎቶ ዘ-ሐበሻ)

በቃጠሎው የወደመው ሳብሪና ግሮሰሪ
(ፎቶ ዘ-ሐበሻ)


በተለይ በመቶዎች የሚቆጠሩ ሕፃናትን ማስተናገድ የሚችለው ‘ሃምዲ የህፃናት መዋያ’ በቃጠሎው ወቅት ምንም ዓይነት ሰው በውስጡ ባለመኖሩ አንዳችም ጉዳት በሰው ሕይወት ላይ አለመድረሱ መልካም ቢሆንም ንግድ ቤቶቹ በጠቅላላ መውደማቸው፣ እንዲሁም በኢትዮጵያውያን መካኒኮች ለሥራ የተቀመጡ መኪናዎች መቃጠላቸው ብዙዎቹን አሳዝኗል። በአጠቃላይ በጋራዦቹ ውስጥ የነበሩ በግምት ከ30 በላይ የኢትዮጵያውያን መኪኖች በቃጠሎው መውደማቸውን ከጋራዦቹ ባለቤቶች መካከል አንዳንዶቹ ለዘ-ሐበሻ አስረድተዋል።
የ70 ዓመት ዕድሜ እንዳለው የሚነገርለት ይኸው ኢትዮጵያውያኑ በብዛት የንግድ ቤት ከፍተው የሚሰሩበት ይኸው ህንፃ የቃጠሎው መነሻ ምን እንደሆነ ባይታወቅም የህንፃው አስተዳዳሪ ጄፍ ባርኔት ለጋዜጠኞች “ቃጠሎው በደረሰበት ወቅት ምንም ዓይነት ሰው አልነበረም፤ በሰው ሕይወት ላይ የደረሰ አደጋ የለም። የእሳቱን መነሻም ምን እንደሆነ አላወቅኩም” ሲል ተናግሯል።
በቃጠሎው መኪኖቻቸው ከወደመባቸው የኢትዮጵያውያን የንግድ ቤቶች ውስጥ የገመቺስ ጋራዥ ባለቤት አቶ ገመቺስ ጋራዡ ሙሉ በሙሉ መውደሙን እና 7 መኪኖቹም አብረው መቃጠላቸውን ለዘ-ሐበሻ ተናግሯል።
ይህ የእሳት ቃጠሎ ከኢትዮጵያውያኑ የንግድ ቤቶች በተጨማሪ 200 ጫማ ርቀት ላይ የሚገኘውን የሬድዮ ምሰሶ አውድሟል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ ዘ-ሐበሻ በሚኒሶታ ለሚገኙ ነዋሪዎች በእሳት አደጋው ንብረታቸውን ላጡ ወገኖቻቸን ጎን በመቆም እርዳታ በማድረግ እንዲተባበር ጥሪዋን ታቀርባለች።
ቃጠሎው የንግድ ቤቶቹን እንዲህ አውድሟል (ፎቶ ዘ-ሐበሻ)

ቃጠሎው የንግድ ቤቶቹን እንዲህ አውድሟል
(ፎቶ ዘ-ሐበሻ)

(በቃጠሎው የወደሙ መኪኖች) ፎቶ ዘ-ሐበ4ሻ

(በቃጠሎው የወደሙ መኪኖች) ፎቶ ዘ-ሐበ4ሻ

ከቃጠሎው በኋላ የሚኒያፖሊስ እሳት አደጋ አካባቢውን እንዲህ አድርጎ አጥሮ ጉዳዩን እያጣራ ነው።

ከቃጠሎው በኋላ የሚኒያፖሊስ እሳት አደጋ አካባቢውን እንዲህ አድርጎ አጥሮ ጉዳዩን እያጣራ ነው።

ልክየለሽ ራስ-ወዳድነት ሰላምና ነፃነትን የሩቅ ህልም እንዳያደርግብን –ከዳኛቸው ቢያድግልኝ

0
0

ethiopian ego
‘ኢጎ’ (Ego) ቃሉ ከግሪክ የተወሰደና ትርጉሙም ‘እኔ’ ወይም ‘እኔነት’ ማለት ነው። ‘እኔ’ና ‘እኔነት’ ራስን ማወቅ፣ መሻትና አሻራ መተውን ደምሮ ህልውናን የሚገልጽ የንቃተ ህሊና አካል ነው። ይህ ስሜት መጠኑን ሲያልፍና ሌላውን አሳንሶ ራስን መሪ፣ አለቃ፣ ቀዳሚ፣ አዛዥ አድርጎ መቁጠር ሲጀመር ወደ (egoist, narcissist) ግለኝነት እኔ ብቻ ወደ ማለት ያድጋል። ነገር ግን ‘ኢጎ’ን በጥቅሉ መጥፎ ቅንፍ ውስጥ መጨመርም ስህተት ይሆናል። ምክንያቱም አኔነትን ማለትም እራስን ማወቅ መሰረታዊና አስፈላጊ ጉዳይ ነውና። ይህ ጽሁፍ የሚያተኩረው ልክ-የለሽ እኔነት ወይም ራስ-ወዳድነት (egoism) ላይ ነው። በርካቶችን “ከእኔ በላይ ለአሳር” በሚያሰኝና እንኳን የሚመኙትን ስልጣን ማጣት የሚኖሩበት አገር መፍርስም ቢሆን እንኳ ከመቻቻል ይልቅ ተያይዞ ገደልን የሚያስመርጥ ውስጣዊ ስሜት ያንጸባርቃሉ። ይህም ጽሁፍ በዚህ ላይ ያተኮረና መፍትሄም አመላካች ይዘት ያለው መልዕክት የማቅረብ መኩራ ያደርጋል። ኢጎ ከልክ ያለፈ ሲሆን ግን ሰው እራስ ወዳድ የሆነና በአህያ እንደተረተው እኔ ካለሁ ሁሉም ለኔ ይኑር አዝማሚያ ያለው “እኔ ከሞትኩ ሰርዶ አይብቀል” አለች እንደሚሉት አይነት ባህሪይን ያላብሳል። ሥዕሉ ይህንን ሀሳብ በመጠኑ ይገልጸዋል የሚል እምነት አለኝ።

(ሙሉውን በPDF ለማንበብ እዚህ ይጫኑ)

የሚሊዮኖች ድምጽ ለነፃነት ዘመቻ እና የመቀሌያችን መታፈን ከነመፍትሄው! ግርማ ሞገስ

0
0
ግርማ ሞገስ (girmamoges1@gmail.com)
ሰኞ ሐምሌ 29 ቀን 2005 ዓ.ም. (August 5, 2013)

 

Girma Mogesግርማ ሞገስ
የሚሊዮኖች ድምጽ ለነፃነት ዘመቻ ወደፊት በመገስገስ ላይ ይገኛል። አንድነቶች የኢትዮጵያን ጸረ-ሽብር ህግ ለማሰረዝ የዜጎች ፊርማ በማሰባሰብ ዘመቻ ላይ ናቸው። የቀድሞውን የግብጽ ፕሬዘዳንት ሞርሲን ከስልጣን የማውረድ እንቅስቃሴ ያስጀመረው ከአስራ አምስት ሚሊዮን በላይ የሚገመተው የግብጾች ፊርማ ከተለያዩ ከተሞች የተሰበሰበው በሶስት ወሮች ነበር። በግብጾች አይን ሲታይ አንድነቶች በሶስት ወሮች አንድ ሚሊዮን ፊርማ ማሰባሰብ አይችሉም ብለን መገመት ያዳግተናል። እርግጥ ኢትዮጵያውያን በሰላማዊ ትግል ባህል እና ክህሎት እንደ ግብጾች ብዙ አልዘለቅንም። ይሁን እንጂ ካሰብነው ቁጥር እንደምንደርስ ጥርጥር የለኝም። የአንድነት መሪዎች መታሰር ቢደርስባቸውም የሚሊዮኖች ድምጽ ለነፃነት የመጀመሪያው ዘመቻ በጎንደር እና በደሴ ከተሞች ሐምሌ 7 ቀን በስኬት ተፈጽሟል። በጎንደር እና በደሴ ከተሞች የዜጎች ፊርማዎች ተሰብስበዋል።

 

ባለፈው ሳምንት ደግሞ አንድነቶች የየከተሞች አስተዳዳሪዎች እና የጸጥታ ኃይሎች የሚፈጽሙባቸውን የወከባ፣ የመኪና ጎማ በማስተንፈስ መጓጓዣ የማሳጣት፣ የቢሮክራሲ ጫና፣ የአካል ድብደባ እና እስር የተለመደ ጽዋቸውን በቻይነት እና በሆደ ሰፊነት በመቀበል እሁድ ሐምሌ 28 ቀን ከመቀሌ በስተቀር በወላይታ፣ በጂንካ፣ በአርባምንጭ እና በባህርዳር ሁለተኛውን ዘመቻ በስኬት አጠናቀዋል። ይኽን በውጣ ውረድ የተሞላ ዘመቻ አንድነቶች ሳይታክቱ፣ በትዕግስት፣ በፅናት፣ በአርቆ አስተዋይነት እና በድስፕሊን በታነጸ አኪያሄድ ፈጽመዋል። አንድነቶች “አንድነት ፓርቲ ሳይገድል እየሞተ ህገ-መንግስቱን የማስከበር ትግሉን አጠንክሮ ዛሬም ወደፊትም ይቀጥላል፡፡” የሚሉትን መርሃቸውን ምንም ሳይሸራረፍ በተግባር እየፈጸሙት ነው። ከህዝባቸው ጋር ታግለው ህዝባቸውን የመብቱ ባለቤት ለማድረግ ያላቸውን ቁርጠኛነት እያሳያዩን ነው። ሊመሰገኑ ይገባል። በአንድ ድንጋይ ሁለት ወፍ እንደሚባለው በአንድ ወገን ፀር-ሽብር ህጉን ለማሰረዝ ሰላማዊ ትግል ዘመቻ ስታደርጉ በሌላ በኩል ደግሞ ከቀድሞው የመገዳደል የፖለቲካ ትግል ባህላችን ወደ ሰላማዊ ፖለቲካ ትግል ባህል ልታሸጋግሩን ታሪክ እየሰራችሁ ነው። ይኽን ሁሉ የምታደርጉት በአስጨናቂ እና በተስፋ አስቆራጭ ሁኔታ ውስጥ እንደሆነ ህዝባችሁ ይረዳዋል። የኢትዮጵያ ጉዳይ የሚያሳስበው በአገር ውስጥ እና ካገር ውጭ የሚኖረው ህዝባችሁ ስራችሁን በአክብሮት፣ በአድናቆት እና በኩራት እያስተዋለ ነው። በስራችሁ እና በስኬታችሁ ልትደሰቱ ይገባል። ታሪክ እየሰራችሁ ነው።

 

በጅንካ፣ በባህርዳር፣ በአርባምንጭ የምትኖሩ ዜጎቻችም ሐምሌ 28 ቀን ባደባባይ ወጥታችሁ፥ “የታሰሩ የፖለቲካ እና የነፃ ጋዜጣ እስረኞች ይፈቱ! መንግስት ህገ-መንግስቱን ያክብር! መንግስት በኃይማኖት ጉዳይ ጣልቃ መግባቱን ያቁም! ውሸት ሰልችቶናል! ይቁም!!! የጸረ – ሽብር ህጉ ባስቸኳይ ይሰረዝ! ዘርን መሰረት ያደረገ ማፈናቀል ባስቸኳይ ይቁም!! የዜጎች ሰብአዊ መብቶች ይከበር!! መብት መጠየቅን ከጸጥታ እና ከልማት ጋር ማያያዝ በአስቸኳይ ይቁም! የፓርቲ አባልነት በፍላጎት መሆን አለበት!!” በማለት የሰብዓዊ መብት ይከበር መልዕክቶች አሰምታችኋል። እነዚህ መልዕክቶቻችሁ እና ጥያቄዎቻችሁ የጅንካ ወይንም የአርባምንጭ ወይንም የባህርዳር ብቻ አይደሉም። የኢትዮጵያ ህዝብ ጥያቄዎች ናቸው። የአለም ህዝብ ጥያቄዎች ናቸው። የተባበሩት መንግስታትም እንዲከበሩ የሚታገልላቸው መሰረታዊ መብቶች ናቸው። በትናትናው ዕለት በወላይታ የሚኖሩ ዜጎቻችንም ስለአገራቸው አሳሳቢ ጉዳዮች በአደባባይ ተሰባስበው ተወያይተዋል። ሰላማዊ ትግላቸውን አጠናክረው እንደሚቀጥሉ አስታውቀዋል። ስለዚህ በጅንካ፣ በአርባምንጭ፣ በባህርዳር እና በወላይታ የምትኖሩ ወንድሞች እና እህቶች በሙሉ ሐምሌ 28 ቀን ባደረጋችሁት የጥሩ ዜጎች ስራ ልትደሰቱ እና ልትኮሩ ይገባል።

 

በዚሁ ባለፈው ሳምንት ህውሃት በመቀሌ ድምጽ ማጉያ እንዳይሰማ በማድረግ እና አንድነቶችን በማሰር የታቀደው የመቀሌ የሚሊዮኖች ድምጽ ለነፃነት ዘመቻ እንዳይሳካ አድርጓል። አምባገነኖች ከጠብመንጃ ይልቅ ነፃ ፕሬስ እንደሚፈሩ እናውቃለን። ባለፈው ሳምንት ግን በመቀሌ አምባገነኑ ህውሃት የድምጽ ማጉያ ሲያፍን አስተዋልን። ድምጽ ማጉያ አይገድልም።  ህውሃት ግን ለምን ድምጽ ማጉያ ይፈራል? ድምጽ ማጉያ እንደ ነፃ ፕሬስ ከአንድ ሰው የሚተላለፍን መልዕክት ለብዙ ሰዎች በአንድ ጊዜ እንዲደርስ ያደርጋል። አምባገነን ህውሃት የፈራውም እሱን ነው። ስለዚህ የሰብዓዊ መብት መከበርን አስፈላጊነት የሚቀሰቅስ የድምጽ ማጉያ ከሐምሌ 25 ቀን ጀምሮ በመቀሌ ስራ ላይ እንዳይውል ተደረገ በህውሃት። በተጨማሪ የአንድነቶችን የቅስቀሳ ቁሳቁሶች ህውሃት በአደባባይ በፖሊስ አስነጠቀ። በቅስቀሳ ላይ የነበሩትን የአንድነት ፓርቲ ብሄራዊ ምክር ቤት አባል አቶ እንግዳ ወ/ፃዲቅ እንዲሁም የትግራይ ዞን የአንድነት ፓርቲ አመራር አባል የሆኑትን አቶ ክብሮም ብርሃነ እና አቶ አርአያ ፀጋይን አሰረ።  የመቀሌ ህውሃት አስተዳዳሪ እና የጸጥታ ኃይሎች እነዚኽን እና ሌሎች ማለቂያ የሌላቸው መሰናክሎችን በመፍጠር የሚሊዮኖች ድምጽ ለነፃነት ዘመቻ በመቀሌ እንዳይሳካ አድርጓል። ህውሃት የመቀሌን ህዝብ አሳብ በነፃነት የመግለጽ ህገ-መንግስታዊ መብት ጥሷል። ወንጀል ፈጽሟል።

 

እንግዲህ ህውሃት እና ሰብዓዊ መብት የሚሰብኩ ድምጽ ማጉያዎች፣ ህውሃት እና ሰብዓዊ መብት የሚሰብኩ መኪናዎች፣ ህውሃት እና ሰብዓዊ መብት እንዲከበር የሚጠይቁ በራሪ ወረቀቶች እሳት እና ጭድ መሆናቸውን ባለፈው ሳምንት በመቀሌ ህውሃት ወለል አድርጎ እንዲታየን አድርጓል። ህውሃት እና ሰብአዊ መብት እሳት እና ጭድ ናቸው። ግን ለምን? ከፍ ብለን እንዳነበብነው ደግሞ አንድነቶች በአንድ ወገን ፀረ-ሽብር ህግ ለማሰረዝ  ሰላማዊ ትግል ዘመቻ ሲያደርጉ እግረመንገዳቸውን በኢትዮጵያ ከቀድሞው የመገዳደል የፖለቲካ ትግል ባህል ወደ ሰላማዊ የፖለቲካ ትግል ባህል ሽግግር መሰረት እየጣሉ ነው። በዚህስ ረገድ ምን ይደረግ? ስለሆነም የዚኽ ጽሑፍ ግብ (1ኛ) ህውሃት እና ሰብዓዊ መብት ለምን እሳት እና ጭድ ሆኑ? እና (2ኛ) የፖለቲካ ትግል ባህል ሽግግሩ ሳያቋርጥ እንዲዳብር እና በህዝባችን ዘንድ እንዲሰርጽ ምን እናድርግ? ለሚሉትን ሁለት መሰረታዊ (መርህ ነክ) ጥያቄዎች መልስ መስጠት ነው።

 

(1ኛ) ለምን ህውሃት እና ሰብዓዊ መብት እሳት እና ጭድ ሆኑ? የመግደል አቅም የሌላቸውን እንደ ድምጽ ማጉያ አይነት ቁሳቁሶችን ህውሃት ለምን ሊፈራ ቻለ? ለሚለው ጥያቄ መልስ እንስጥ።

 

የመንግስት ስልጣን ከምርጫ ሳጥን ይመነጫል የሚለው የፖለቲካ ትግል ባህል በሰላማዊ የፖለቲካ ትግል የሚፈጸም ነው። ህውሃት ይኼን የፖለቲካ ባህል ከወሬ ባሻገር አያውቀውም። ባህሉም የለውም። በነፃ ምርጫ እመረጣለሁ ብሎም አያምንም። የመንግስት ስልጣን ከጠብመንጃ አፈሙዝ ይመነጫል የሚለው እርስ በርስ መጨራረስን በይፋ የሚሰብከው ፍልስፍና ነው የህውሃት የፖለቲካ እምነት። ህውሃት ተወልዶ ያደገው ይህን የፖለቲካ እምነት በመከተል እና በመፈጸም ነው። ይኽ የፖለቲካ ፍልስፍና ደግሞ ለስልጣን እንጂ ለሰብዓዊ መብት ዋጋ እንደማይሰጥ ግልጽ ነው። ትጥቅ ትግል እና ሰብዓዊ መብት የተባሉት ሁለት ነገሮች እሳት እና ጭድ ናቸው። ባጭሩ ትጥቅ ትግል እየሰብክ እና እያራመድክ ሰብዓዊ መብት አክባሪ ነኝ አትበለኝ ነው የምልኽ!!!

 

ህውሃት ሳያቋርጥ ለአስራ ሰባት አመቶች በእርስ በርስ ጦርነት ህዝብ አጫርሶ፣ መንደሮች አፍርሶ እና ህዝብን ለስደት ዳርጎ ለስልጣን የበቃ ድርጅት ነው። እንደሚታወቀው ህውሃት ቲ.አል.ኤፎችን በተኙበት አርዶ፣ ኢ.ዲዩ.ዎችን፣ ኢህአፖችን እና የደርግን ወታደሮች ፈጅቶ ነው እዚህ የደረሰው። በትግራይም ህውሃትን ከተቀላቀሉ ወጣቶች ውስጥ ወደ ቤተሰቦቻቸው መመለስ የፈለጉን በአረመኔነት ገድሎ፣ በውስጡም ቢሆን ከአምባገነኖቹ መሪዎቹ የተለየ አሳብ የነበሩዋቸውን አባላቱን እየፈጀ፣ ገበሬውን ስደተኛ እያደረገ፣ የውጭ እርዳታ ለማግኘት ድርቅ እልቂት በአረመኒነት እንዲባባስ እያደረገ ነው ለስልጣን የበቃው። ይህ ሁሉ ተግባሩ ህውሃትን የሰብዓዊ መብት አፍራሽነት የሻምዮንነት ማዕረግ ያስገኝለታል። ህውሃት እና ሰብዓዊ መብት እሳት እና ጭድ ናቸው።

 

ህውሃት ስልጣን ላይ ከወጣም ወዲህ አገር አፈረሰ። የባህር በር አሳጣን። የአልቢኒያ እና የሶቪየት ህብረት አምባገነኖች የጻፉትን ቃል በቃል ቀድቶ ኢትዮጵያን ሊያስተዳድር ሞከረ። አልሰራ ሲለው በሽብር በማስተዳደር ላይ ይገኛል። የአገሩን ህዝብ ታሪክ ጠንቅቆ አውቆ፣ ቀደም ብለው የተፈጸሙ ስህተቶችን አስተካክሎ እና እንዳይደገሙ አድርጎ ህዝቡን አቀራርቦ አገር በመምራት ላይ የሚገኝ ቡድን አይደለም።

 

ስለዚህ ባለፈው ሳምንት ህውሃት በመቀሌ እና በሌሎች ከተሞች የፈጸማቸውን እንቅፋቶች እና ወደፊት ሰላማዊ ትግላችንን ለማራማድ በምናደርገው ጥረቶች ከህውሃት በኩል የሚገጥሙን ፈተናዎች ምንጫቸው ይህ የህውሃት ከሰብዓዊ መብት ማክበር ባህል ጋር እሳት እና ጭድ መሆኑ እንደሆነ መዘንጋት የለበንም። በህገ-መንግስቱ ውስጥ የተዘረዘሩት ሰብዓዊ መብቶችም ቢሆኑ የምዕራቡን አለም ለማጭበርበር እና የገንዘብ እርዳታ ለማግኛ እንጂ አምባገነኑ መለስም ሆነ ዛሬ ኢትዮጵያን የሚያስተዳድረው የመኪና ጎማ አስተንፋሽ ወሮበላ ህውሃት ፍጽም አያምንባቸውም። ህውሃት የፖለቲካ ባህሉ መግደል ነው። ስብዕናው የተሟጠጠ ነው። ታሪኩ ደም ነው። ስለዚህ ህውሃት በኢትዮጵያ ዲሞክራሲ ስርዓት መገንባት የሚያስችለው ባህል ፍጹም የለውም። በዚህ ሁሉ ምክንያት ሰብዓዊ መብት የሚቀሰቅስን የድምጽ ማጉያ ህውሃት ቢፈራ ሊገርመን አይገባም።

 

(2ኛ) የፖለቲካ ትግል ባህል ሽግግሩ ሳያቋርጥ እንዲዳብር እና በህዝባችን ዘንድ እንዲሰርጽ እንዴት እንርዳ? ህውሃት አምባገነን ነው። አምባገነን ይፈራል። ህውሃት በህዝብ ይሁንታ ስልጣን ላይ አልወጣም። ህጋዊነት እንደሌላቸው ህውሃቶች ብልቦናቸው ያውቁታል። ስለዚህ ከጠበንጃ ይልቅ ህዝባዊ ነፃ መሰባሰብን፣ ህዝባዊ ነፃ ውይይትን እና ህዝባዊ ተሳትፎን ይፈራሉ። ህዝቡ በነፃነት የሚያደርጋቸው ነገሮች አምባገነኖችን ያስደነግጧቸዋል። ያስበረግጓቸዋል። የኢትዮጵያ ህዝብ ሰላማዊ ትግል ወታደሮች ነን የምንል ሁሉ እነዚህን የአምባገነኖች ሁሉ መለያ መሰረታዊ ጸባዮች ጠንቅቀን ልናውቅ ይገባል። የፖለቲካ ትግል ባህል ሽግግር ቀላል እንደማይሆንም በቅድሚያ ልንገነዘብ እና ልንዘጋጅ ይገባል። የሰላም ትግል ሰራዊት ትግባሮች ድርብርብ ናቸው። ለምሳሌ የሚሊዮኖች ድምጽ ለነፃነት ዘመቻ ለማኪያሄድ እንኳን አንድነቶች የሰላማዊ ትግልን ባህል ለህዝብ ከማስተዋወቅ በተጨማሪ በየከተማው የሚገኙ የህውሃት አስተዳዳሪዎች እና የፀጥታ ኃይሎችን ሲያግባቡ፣ ሲቻል ሲያላምዱ፣ እንዳይፈሩ እና በተወሰነ ደረጃም ቢሆን እንዲያምኑዋቸው ሲጥሩ፣ ወደ ድርድር እንዲመጡ ሲያበረታቱ እና የመሳሰሉትን  ሲያደርጉ አይተናል። እንደ አስፈላጊነቱም የተመጠነ ‘የጀግኖች’ መውጫ በር መስጠት ሊያስፈልግ ይችላል። ይኽ ሁሉ መቼ መደረግ እንዳለበት እና እንደሌለበት እና የትኛው መቅደም እንዳለበት ማወቅ ያስፈልጋል።

 

የፖለቲካ ትግላችንን ባህል ሽግግር ለማፋጠን ህውሃትን የተጀመረው የፖለቲካ ባህል ሽግግር አካል ማድረግ ለሁላችንም ይጠቅማል። ይኽን ለማድረግ ሰለአምባገነኖች ፀባይ ከፍ ብለን የዘረዘርናቸውን ማወቅ እና ተገቢውን ስራ መስራት ይጠቅማል። የሰላማዊ ትግላችን ግብ ህውሃትን ለመበቀል አይደለም። በፍጹም። የሰላም ትግል ወታደር ግቦች ህዝባችንን ወደ ነፃነት፣ ዲሞክራሲ እና ልማት ማሸጋገር ነው። ይኽን ከስኬት ለማድረስ እራስን በዘመናዊ ሰላማዊ ትግል ንድፈ አሳብ እና አፈጻጸም መቃኘት ያስፈልጋል። እንደትናንቱ በሰላማዊ ትግል መዝገበ-ቃላት ትርጉሙ ብቻ መወሰን በቂ አይደለም። የሰላማዊ ትግል ክህሎታችንን ማዳበር አለብን።

 

ስለዚህ የመቀሌ አንድነቶች የወሰናችሁት የማፈግፈግ ውሳኔ የሚያመለክተው ብስለታችሁን እንጂ መሸነፋችሁን  አይደለም። በማፈግፈግ የሰላም ትግል ሰራዊትን ለነገ ማቆየት ጠቃሚ ነው። ይኽን አይነቱ  ማፈግፈግ መፍራት አይደለም። የሰላም ትግል ሰራዊት በመቀሌ ያላጠናቀቀው ተጨማሪ ስራ መኖሩን ተገንዝቦ ሰልፉን ወደፊት ማስተላለፉ አኩሪ እርምጃ ነው። አንድነቶች በመቀሌ የደረሰባችሁ ጠንካራ እንቅፋት እና ያደረጋችሁት አይነት ማፈግፈግ እነ ጋንዲም በዘመናቸው ትግላቸውን ወደ አዳዲስ ከተሞች ለማሰራጨት ጥረት ሲያደርጉ ደርሶባቸዋል። አፈግፍገዋልም። አንድነቶች ሰላማዊ ትግላቸውን በመቀሌ አጠናክረው እንደሚቀጥሉ እና መስከረም 2006 ዓ. ም. ከመግባቱ በፊት ስኪታማ ሰላማዊ ሰልፍ እንደሚያደርጉ ጥርጥር የለኝም። ካለፈው ሳምንት አንድ ነገር ተምረናል። በመቀሌ የተሳካ ሰላማዊ ሰልፍ ለማድረግ እንደ ጅንካ፣ አርባምንጭ ወይንም ባህርዳር የአንድ እና ሁለት ቀን ቅስቀሳ እንዲሁም የጥቂት አንድነቶች ስምሪት ብቻ በቂ አይደለም። መፍትሄው ዘመቻውን ማጠናከር ነው። ተጠባባቂ ኃይል መመደብ ሊያስፈልግም ይችል ይሆናል። የስለማዊ ትግሉ ነፋስ ከመቀሌ ተነስቶ ወደ አክሱም እና አዲግራትም እንዲነፍስ ማድረግ ይጠቅማል። በመቀሌ የተከማቸውን የህውሃት ኃይል ለመበተን።

 

በአንድ ወገን የሚሊዮኖች ድምጽ ለነፃነት ዘመቻ በመቀሌና በቀሩት ከተሞች እንዲቀጥል ስንታገል በሌላ በኩል  ህውሃት አንድነት ፓርቲን ለመወንጀል እና ክትግል ሜዳ ለማስወጣት የማይፈነቅለው ድንጋይ እንደማይኖርም ከወዲሁ መገመት እና መከላከያውን ማዘጋጀት ይኖርብናል። ይኽን ምኞቱን ለማሳካት ህውሃት የተቻለውን በማድረግ ላይ ስለመሆኑ ባለፈው ሳምንት በወላይታ የአንድነት ፓርቲ የዞን አመራር አባል በሆነችውን በወ/ሮ ሀድያ መሀመድ ላይ የፈጸመው ተቋሚ መረጃ ነው። ህውሃት ካለ ምንም ምክንያት ወ/ሮ ሀድያ መሀመድን ካሰረ በኋላ የአንድነት ፓርቲ ህዝበ ሙስሊሙን ለአመፅ ያነሳሳል የሚል ሰነድ እንድትፈርም አግባባት። እምቢ አለች። ከዚያ ህውሃት ሊያስገድዳት ሞከረ። በኢንቢታዋ ጸናች። እስሩ ቀጥሏል። አንድነቶች ህውሃት ሊቀድማችሁ አይገባም። ለምሳሌ በወ/ሮ ሀድያ መሀመድ ላይ የተፈጸመውን በአገር ቤት እና በውጭ የሚኖሩ ዜጎች እንዲሁም ዲፕሎማቶች እንዲያውቁት ሰፊ ዘመቻ ማድረግ ይጠቅማል። ህውሃትን ተአማኒነት ለማሳጣት። ሌላም ይደረግ። ይኽ ፍራቻ አይደለም። ጀግኖች የሚያደርጉት ጥንቃቄ ነው። አንድነቶች በርቱ!!!

 

አንባቢዎች ሆይ! አንድነቶች ፀረ-ሽብር ህግን ለማፍረስ እና የፖለቲካ ትግል ባህላችንን ለመቀየር የጀመሩትን ዘመቻ እንቀላቀል። እንርዳቸው! የተጀመረው አዲስ ታሪክ አካል እንሁን!!! የሚከተሉትን በማድረግም በመሰራት ላይ ባለው ታሪክ ማህተማችንን ማስቀመጥ እንችላለን።

 

እርዳታ፥ በገንዘብ!
እርዳታ፥ በአሳብ!
እርዳታ፥ መረጃዎች በፍጥነት በማሰራጨት!
እርዳታ፥ ፊርማዎች በማሰባሰብ!
እርዳታ፥ እንደገና በገንዘብ!
ድረ ገጻቸው፥ www.andinet.org

 

 

 

መንግስት ከ4 ዓመት በኋላ በፀረሽብርተኝነት ህጉ ላይ የውይይት መድረክ አዘጋጀ

0
0

አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ የፀረ ሽብርተኝነት ህጉን ለማሻር የጀመረው የፊርማ ማሰባሰብ ዘመቻ በሀገር ውስጥና በአለም አቀፍ ደረጃ ተቀባይነት ማግኘቱንና የመዋያያ አጀንዳ መሆኑን ተከትሎ የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ድርጅት ህጉ ከፀደቀ ከ4 ዓመት በኋላ ፓርቲዎች በህጉ ላይ ያላቸውን አቋም የሚያስረዱበት መድረክ አዘጋጀ፡፡
ኢቲቪ አንድነት ፓርቲን ጨምሮ ለተለያዩ ፓርቲዎች ደብዳቤ የላከ ሲሆን አንድነት ፓርቲ በበኩሉ በ5 የክልል ከተሞች ለሚያደርገው ህዝባዊ ንቅናቄ አመራሮቹን ስላሰማራ የውይይት መድረኩ እንዲራዘምለት ጥያቄ አቅርቧል፡፡ አንድነት ፓርቲ የሚሊዮኖች ድምፅ ለነፃነት በሚል መሪ ቃል የጀመረው ህዝባዊ ንቅናቄ በስኬት እየተካሄደ መሆኑ ይታወቃል፡፡ #millionsofvoicesforfreedom #Ethiopia #UDJ - 

unity-c2 unity c

 


ESAT Daliy News August 05 2013 Ethiopia

የእናት ዓለም ደሴ ፍጻሜ አልባ እንባ…

0
0

አቡ ዘኪያ
ከምድረ አናቶሊያ

ኧረ ደሴ ደሴ …ደሴ ላኮመልዛ

ምን አንልህ አንድዬ መከራችን በዛ
dese
የመቶ ሃያ ሰባት ዓመት እድሜ ባለጸጋዋ…በዉበት መፍለቂያ አምባዎች ስር የተሸጎጠችው የደሴ ከተማ ዛሬም እንደ ትናንቱ ታነባለች…መስከረም 17 ቀን 1909 የመስቀል እለት ነው አሉ ደሴን መናገሻቸው ላደረጉት የሰሜኑ ንጉሥ ሚካኤል “ልጅዎ ልጅ ኢያሱ ላይ መፈንቅለ መንግሥት ተደርጓል::እርሱም የት እንደደረሰ አይታወቅም::”የሚል አንድ ቤትና ጨርቅ አስጥል የስልክ መልእክት ከወደ አዲስ አበባ የደረሳቸው::ደዋይዋ የወቅቱ የውጭ ሥራና የንግድ ሚኒስትር ቢትወደድ ኃይለ ጊዮርጊስ ወልደ ሚካኤል ባለቤትና የንጉሥ ሚካኤል ልጅ ወይዘሮ ስኅን ነበሩ::Water shortage in Desse, Ethiopia

አዛውንቱ ንጉሥም ብዙም ሳይመክሩ “ወላድ ፍረደኝ የጠፋ ልጄን አፋልገኝ” በሚል አንጀት-በላ ዲፕሎማሲያዊ የክተት አዋጅ የደሴና አካባቢዋን ጎበዛዝት አስከትተው በደመ ነፍስ ወደ ሸዋ ገሰገሱ::በለስ ቀናቸውና ጥቅምት 7 ቀን 1909 በራስ ሉልሰገድ የተመራውን የሸዋ ጦር ቶራ መስክ ላይ ድባቅ መቱት::”ሲያልቅ አያምር” እንዲሉ ከአስር ቀን በኋላ ድል እድል ነሳቻቸውና ሰገሌ ላይ በሸዋ ጦር ድል ተነስተው ተማረኩ::አየ የቀን ክፉ …አዛውንቱ ንጉሥ ሚካኤል…የአድዋው ጀግና ንጉሥ ሚካኤል ልክ እንደ ልጃቸው ካልጋ ላይ ወደቁና አረፉት ::ለይህም እኮ ነው የደሴ አዝማሪ እንዲህ ሲል ያንጎራጎረው:-

ወይ እነሱ አያውቁ

ወይ ሰው አይጠይቁ

አባትና ልጁ ካልጋ ላይ ወደቁ

ንጉሡ ቢማረኩም ሰራዊታቸው እጅ አልሰጠም::በልጅ ኢያሱ ይደገፉ የነበሩ የንጉሥ ሚካኤል የጦር አበጋዞች ደሴ ላይ መሽገው ለወራት የሸዋን ጦር ቁም ስቅሉን አሳዩት::የኋላ የኋላ መዳከም መጣና ደሴ በሸዋ ጦር እጅ ወደቀች::,የሸዋም ጦር አንድ ሐበሻ በሌላ ሐበሻ ላይ ይፈጽመዋል ተብሎ የማይጠበቅ ጭፍጨፋ በደሴ ሕዝብ ላይ ፈጸመ::ደሴ እንደ ችቦ ነደደች…አምርራም አነባች…የሕዝባቸውን መከራ ዝዋይ ደሴት እስር ላይ ሆነው የሰሙት አዛውንቱ ንጉሥ ሚካኤልም እንዲህ ብለው ስንኝ ቋጠሩ አሉ:-

ደግ ነገር ሳለ ክፉ ተናግሬ

ያገር ልጅ እያለ ከባሪያ መክሬ

አቃጠሉት መሰል ሸተተኝ ሀገሬ

የደሴ መከራ መች እንዲህ በዋዛ ሊያበቃ…በወርኅ መስከረም 1928 ጣሊያን ሀገራችንን ዳግም ወረረ::ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴም ክተት ሰራዊት ምታ ነጋሪት ብለው ወደ ሰሜን አመሩ::የጦር ሰፈራቸውንም ደሴ በሚገኘው ቪላ ኢታሊያ ወይም መርሆ ግቢ በሚሰኘው የአልጋ ወራሽ አስፋ ወሰን ኃይለ ሥላሴ ቤተመንግሥት ዉስጥ አደረጉ::በመሆኑም ደሴ የፋሽስት ጣሊያን የጦር አውሮፕላኖች ዋና ኢላማ ሆነች::

ዋቢ መዛግብቶች እንደሚያወሱት ከኅዳር እስከ የካቲት 1928 ባሉት ሦስት ወራት ዉስጥ ብቻ ደሴና ሕዝቧ ስምንት ከባድ የአየር ድብደባዎችን አስተናግደዋል::ደሴ ላይ የወረደውን የቦምብ ዶፍ አስመልክተው ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ “ሕይወቴና የኢትዮጵያ እርምጃ” በተሰኘው ግለ-ታሪክ ድርሳናቸው ላይ “ህዳር 26 አርብ ጧት 1928 ሃያ አንድ አውሮፕላኖች መጥተው ቦምብ ያዘንብቡን ነበር…እንደሚጥሉት ቦምብ ትልቅነትና ብዛት በደሴ ከተማ የሰው ዘር የሚተርፍ አይመስልም ነበር::”በማለት ነበር የደሴን አበሳ የገለጹት::በወቅቱ ጦርነቱን ለዓለም ሕዝብ ለመዘገብ ደሴ ከትመው ከነበሩት የውጭ ጋዜጠኞች አንዱ የነበረው ጆርጅ ስቲር Caesar in Abyssinia በተሰኘው በዚያው ሰሞን በታተመው መጽሐፉ የኅዳር ሃያ ስድስቱን ድብደባ አስመልቶ እንዲህ ይለናል “The casualities were heavy,for the bombardment was quite unexpected.Fifty three were killed,many by burning in their huts,and about two-hundred killed in crowded Desseye.The people of Desseye were crazy with fear and rage:as the planes circled round,the town seethed as a furious hive.” አየ አለመታዴል ዴሴ ነዴዴች…

እ.አ.አ. ሚያዝያ 15 ቀን 1936 ከፈታኝ ዉጊያ በኋላ ስትራቴጂካዊዋ የብሶት ከተማ ደሴ ፋሽስቶች እጅ ላይ ወደቀች::የፋሽስቱ ጦር የሰሜን ግንባር አዛዥ ፊልድ ማርሻል ባዶሊዮም The War in Abyssinia በተሰኘው መጽሐፉ ላይ እንዲህ ሲል ጻፈ “the last and bloodiest of all the battles came to an end at Dessie” አዎ ደሴ እንደ ወትሮው በደም ታጠበች…አምርራም አነባች…

በብርሃን ፍጥነት ወደ 1965….

1960 ልክ እንደ ዛሬው የዓረቦች ጸደይ ወጣት አብዮተኞች አውራ ጎዳናዎችን የተቆጣጠሩበት ዓመት ነበር::ፓሪስ ቶኪዮ ፕራግና መሰል ከተሞች በወጣት አብዮተኞች ተናወጡ::የኛዋ አዲስ አበባም በግራ ዘመሞቹ የቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች መሪነት የአብዮታዊ ሰልፎች መዲና ሆነች::ከቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ ቀጥሎ ከፍተኛ አብዮታዊ እንቅስቃሴ በማካሄድ የሚታወቀው የደሴው ወ/ሮ ስኅን ት/ቤት ነበር::በእለተ ዓርብ ግንቦት 10 ቀን 1965 በወ/ሮ ስኅን ተማሪዎች መሪነት የደሴ ተማሪዎች ታላቅ ሰላማዊ ሰልፍ አደረጉ::እንዳለመታደል ሆነና ያ ታሪካዊ ሕዝባዊ ሰላማዊ ሰልፍ በደም ተጠናቀቀ::በጠቅላይ ግዛቱ እንደራሴ ደጃዝማች ሰለሞን ኣብርሃ(የፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ አጎት)አዛዥነት የጠቅላይ ግዛቱ ፖሊስ አዛዥ በነበሩት ጄኔራል ዮሐንስ አስፈጻሚነት የንጉሠ ነገሥቱ ፈጥኖ ደራሽ ጦር ሰላማዊ ሰልፈኞች ላይ በመተኮስ 15 ተማሪዎችን በግፍ ሲገድል አያሌዎችን አቆሰለ::የደሴዋ ፒያሳ በደም ታጠበች…ደሴም ስለ ልጆቿ ምርር ብላ አለቀሰች…

ባንድ ወቅት ተማሪዎቹ የነበሩት የወ/ሮ ስኅን ተማሪዎች በግፍ መጨፍጨፋቸውን የሰማው ገጣሚና ቀያኒ ዮሐንስ አድማሱ በወርኃ ጥቅምት 1966 በጻፋት “ዕንባሽ”የተሰኘች ግጥሙ የእናት ዓለም ደሴን ሰቆቃና እንባ ከመጽሐፍ ቅዱሷ ራሔል እንባ ጋር በማነጻጸር እንዲህ ሲል ሰነኘ:-

በዕንባሽ ውስጥ አልፌ በዕንባሽ ተንሳፍፌ

ገና ዳር ሳልወጣ ዕንባሽን ቀዝፌ

ራሄልን በዕንባሽ አየሁዋት በራማ

በዕንባሽ ተቀስቅሳ ታነባለች ቁማ ::

ዘመን ቢያርቃችሁ

ሥፍራ ቢለያችሁ

ዕንባ አጋጠማችሁ

ዋይታ ተሰምቶ ጆሮዬ ተጠማ

ያንች ካለሁበት የራሄል ከራማ

የዋይታ ክብሩ የሙሾውም ቃና

የእሷ የእናትነት ያንች የድንግልና ::

ዘመን ቢያርቃችሁ

ሥፍራ ቢለያችሁ

ዕንባ አጋጠማችሁ

እድሜ ለዚያ ትውልድ አንበሶችና አናብስቶች በየካቲት 1966 ሕዝባዊ አብዮት ፈነዳና የቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ ስርዓት ተገረሰሰ::ምን ዋጋ አለው?!…አብዮታችንን ስልጣንና ደም በጠማቸው ወጥቶ አደሮች ተነጠቅን::ሀገራችንም ከድጡ ወደ ማጡ ዘቀጠች::የኢትዮጵያ ከተሞች የሞት አምባ ሆኑ::ወጣትነት ወንጀል ሆነ::ቀይ ሽብር ታወጀ:: የቀይ ሽብር ግንባር ቀደም ሰለባ ከሆኑት ከተሞች አንዷ ሰርክ-አንቢዋ ደሴ ነበረች::በ1969 መባቻ ላይ በወሎ ክፍለ ሀገር ዋና አስተዳዳሪ ኮሎኔል ጌታሁን እጅጉና በደህንነት ሹሙ ሻለቃ ንጉሤ ቱጂ መሪነት የሕዝብ ድርጅት አባላት በቀበሌና ከፍተኛ የአብዮታዊ ዘመቻ አስተባባሪ ኮሚቴ ነፍሰ ገዳዮች በመታገዝ በደሴ ወጣቶች ላይ “መንጥር” የተሰኘ ዘመቻ አወጁ::

ዘመቻ መንጥር አያሌ የደሴ ልጆችን ለእስርና እንግልት ዳረገ::ይህ በንዲህ እንዳለ ቅዳሜ የካቲት 26 ቀን 1969 ከምሽቱ ሁለት ሰዓት ላይ የወሎ ክፍለ ሀገር የደህንነት ሹምና የዘመቻ መንጥር ጠቅላይ አዛዥ የነበሩት ሻለቃ ንጉሤ ቱጂ በኢሕአፓ አባላት መኪናቸው ላይ በተጠመደ ፈንጂ ሸዋ በር ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ከነአጃቢያቸው ተገደሉ::የደሴ አዝማሪም እንዲህ ሲል አንጎራጎረ:-

ጨካኝ ነበር እርሱ ጨካኝ አዘዘበት

እንደ ቡሄ ዳቦ እሳት ነደደበት

የሻለቃ ንጉሤን ሞት ተከትሎ ሞት ደሴ ላይ ነገሠ::የከተማዋ ጎዳናዎች በደም ታጠቡ…ደም-ምሷ ፒያሳም ሬሣ በሬሣ ሆነች…ደሴም ስለ ልጆቿ ምርር ብላ አለቀሰች…ይህን ግፍ ያየ አዝማሪም እንዲህ ሲል በማሲንቆው አለቀሰ:-

ኧረ ደሴ ደሴ ገራዶ ገራዶ

አለቀልሽ ልጅሽ እንደ በሬ ታርዶ

ግንቦት 10 ቀን 1983…

የግንቦት 10 ቀን 1965 ሰማዕታት አስራ ስምንተኛ ዓመት በሚታሰብበት እለት ሌላ ታሪካዊ ክስተት ደሴ ላይ ተከሰተ::በስድስት ብርጌዶች የተዋቀረው “ብሶት የወለደው” የጀግናው ኢሕአዴግ ቴዎድሮስ ክፍለ ጦር በቀድሞው የወ/ሮ ስኅን ተማሪ ዋለልኝ መኮንን ስም በተሰየመ ዘመቻ ደሴ ላይ መሽጎ የነበረውን 26ኛውን የመንግሥት ሰራዊት ድባቅ በመምታት ደሴን ከደርግ “ነጻ” አወጣ…እድሜ ለዘመቻ ዋለልኝ ደሴ ሰናይ ዘመን መጣ ብላ ፈገግ አለች::ግና ያፈገግታ ያ ተስፋ ወዲያው በኖ ጠፋ::የአዲሱ ገዥ ኃይል አካሄድ ያላማራቸው የታሪካዊው ወ/ሮ ስኅን ት/ቤት ተማሪዎች ሰኔ 3 ቀን 1983 ፒያሳ ላይ ያደረጉት የተቃውሞ ሰልፍ በወያኔ ወታደሮች የመትረየስ እሩምታ ተበተነ::ደም-ምሷ ፒያሳም በደም ታጠበች…ደሴም ስለ ልጆቿ ምርር ብላ አለቀሰች…

የሰኔ 3 ቀን 1983 ጭፍጨፋ ኢሕአዴግ ፊቱን ያዞረ ደርግ መሆኑን ለደሴ ሕዝብ ያረጋገጠ አሳዛኝ ታሪካዊ ክስተት ነበር::ከዚያች እለት ጀምሮ ኢሕአድጋዊያንና ደሴ ሆድና ጀርባ ሆኑ::የደሴ ሕዝብም ምርጫ በመጣ ቁጥር ድምጹን በመጠቀም በኢሕአዴግ ላይ ድምጽ አልባ መፈንቅለ መንግሥት( Silent Coup d’État)ማድረግን የፖለቲካ ባህሉ አደረገው::አብዮታዊ ዴሞክራቱ ኢሕአዴግም በበኩሉ በየምርጫው ዋዜማና ማግሥት የደሴን ሕዝብ ማዋከብና በውኃና መብራት ማዕቀብ ማሰቃየትን የሙጥኝ ብሎ ተያያዘው::

ታኅሳስ 4 ቀን 2004…

“ድምጻችን ይሰማ” የሚል ጩኸት ከወደ አወሊያ ተሰማ::የደሴ ሙስሊሞችም በብርሃን ፍጥነት “አዎ ድምጻችን ይሰማ” ሲሉ ለአወሊያ ተማሪዎች ጥሪ ምላሽ ሰጡ::ዓመት ከስምንት ወር በሆነው የሙስሊም ሐበሾች የነጻነት ትግል ደሴዎች ግንባር ቀደም ሚና እየተጫወቱ መሆኑ አሌ የማይባል ሀቅ ነው:: ይህ በመሆኑም ነው የኢሕአዴግ ዘረኛና መርዘኛ የግፍ በትር የደሴ ሙስሊሞች ላይ በርታ ያለው::ልክ የዛሬ ወር እውቁ የኃይማኖት መምሕር ሸህ ኑር ኢማም በግፍ ተገደሉ:: የሸህ ኑሩን ግድያ ተከትሎ የደሴ ሙስሊሞች ቁም ስቅላቸውን እያዩ ነው::

በአሁኑ ወቅት ደሴ ዉስጥ ሙስሊም መሆን ወንጀል ነው::ሕዝበ ሙስሊሙ የረመዳን ጾምን ያለመብራትና ዉኃ እንዲጾም ተፈርዶበታል::ዘመነ አፈሳ ወ አበሳ ደሴ ላይ ዳግም ነግሷል::የገዥው ኃይል ቅጥረኞች የዓይኑ/ኗ ቀለም ያላማራቸው ሙስሊም ላይ ነጻ እርምጃ እንዲወስዱ በጌቶቻቸው ታዘዋል::ሙስሊሞች ይታሰራሉ ይገረፋሉ ይደፈራሉ ይዘረፋሉ::ወዴት እየሄድን ነው?የመናገር መብታችሁን አስከበርኩላችሁ የሚለን ልማታዊ መንግሥታችን ከመናገር በኋላ ያለውን መብታችንን መቼ ይሆን የሚያከብርልን?መብቴ ይከበር ብሎ መጮህ በየትኛው አዋጅ ነው ወንጀል ተብሎ የተደነገገው?ግራም ቀኝም ገባን ጃል… …በዘመነ መኳንንቱ(ዘመነ አፄ) በዘመነ ሰራዊቱ(ደርግ)እና በዘመነ ደደቢት(ኢሕአዴግ) መሀል ያለው ልዩነት አልታያችሁ አለን’ኮ…ጎበዝ ልብ ያለው ልብ ይበል ደሴ ላይ የመከራ ደመና አንዣቧል…ደሴ እያነባች ነው…ኧረ ለመሆኑ የእናት ዓለም ደሴ ዋይታ ፍጻሜ መቼ ይሆን?

ያ ያዬሁት ዕንባ ከልብሽ ተልኮ
ባይኔ ላይ ሲያዘግም መንፈሴ ታውኮ
የብቸኝነት ቅኔ ሲቀኝ ሰማሁ ቁሜ
ራማ ነው አለኝ የዋይታሽ ፍጻሜ ::

(ዮሐንስ አድማሱ ጥቅምት 1966)

የእናት ዓለም ደሴ ሙስሊሞች ሆይ በሩቁ ከወዲሁ ዒድ ሙባረክ ወኩሉ ዓም ወአንቱም ቢኸይር ብያለሁ!

ማዓ ሰላማህ!

ለንጹሃን የደም ጥሪ ተገቢው ምላሽ ትጥቅ አንስቶ ነፍሰ ገዳዮችን መፋለም ብቻ ነው!

0
0

የግንቦት 7 ሕዝባዊ ኃይል (መግለጫ)
Ginbot 7 Popular Force
GPF_Logo-Small

Ginbot 7 Popular Force logoከሃምሌ 26 _ 2005 አንስቶ ይህ መግለጫ እስከወጣበት እስከ ሃምሌ 28_ 2005 አ.ም እለት የወያኔ ዘረኛ ጉጅሌ ቅጥር ነፍሰ ገዳዮቹን በማሰማራት በመላው ኢትዮጵያ፣ በእስልምና እምነት ተከታይ የሃገሪቱ ዜጎች ላይ በስፋት የግድያ እርምጃ እየወሰደ ነው። ክቡር ህይወታቸውን በግፈኛው የወያኔ የአፈና ሃይል ያጡት ወገኖች ቁጥር በርካታ ሆኗል። ክፉኛ የቆሰሉት ወገኖቻችን ቁጥር ከተገደሉት እጅጉን የገዘፈ ነው። ፍጹም አረመኔያዊነት በተሞላው መንገድ በወያኔ ቅልብ ጦር የተቀጠቀጡትና እንደከብት ተሰብሰብው በየእስር ቤቱ የታጎሩት ወገኖቻችን ቁጥር በሽዎች የሚቆጠር ሆኗል። እጅግ ሰላማዊና ስልጡን በሆነ መንገድ ፍትሃዊ ጥያቄ ባነሱ ወገኖቻችን ላይ የደረሰውን እልቂት የግንቦት 7 ህዝባዊ ሃይል የራሱ እልቂት አድርጎ ያየዋል። የደረሰባቸውን መከራና እንግልት የራሱ መከራና እንግልት አድርጎ ወስዶታል።

የግንቦት 7 ህዝባዊ ሃይል ወያኔን አያወግዝም ወይም ወያኔ በኢትዮጵያውያን ላይ የሚፈጽመውን ግፍ በገንዘብና በስልጠና በዲፕሎማሲ ድጋፍ የሚያበረታቱን የምእራብና ሌሎች የወጭ መንግስታት ከድርጊታቸው እንዲታቀቡ አይማጸንም። ባለፉት 22 አመታት ውግዘትና መማጸን የትም እንዳላደረሱን በሚገባ እናውቃለንና። ግንቦት 7 ህዝባዊ ሃይል ደግሞ ደጋግሞ ግልጽ እንዳደረገው የኢትዮጵያ ህዝብ መከራ የሚያበቃው ህዝብ የወያኔን በእብሪት የተሞላ ግፈኛ ማንነት የሚመጥንና የሚስማማ የትግል ስልት መርጦ አምሮ ወያኔን ታግሎ በመደምሰስ ብቻ ነው። ሙስሊሙም ሆነ የሌሎች እምነት ተከታዮች መረዳት የሚገባን ወያኔ ስላማዊና ስልጡን ከሆነው የእኛ አለምና መርህ ጋር የማይተዋወቅ ዘረኛ ገዳይ ሃይል መሆኑን ነው። ይህ በእብሪትና በድንቁርና የታጀለ የወያኔ ሃይል የእናንተን ትእግስት ከፍርሃት፣ አርቆ አሳቢነታችሁን ከሞኝነት ጋር አስተሳስሮ የሚያይ ነው። “የምንገድልለት አላማ ባይኖረን የምንሞትለት አላማ አለን” የሚለውን ድንቅና ክቡር እመነታችሁን ወያኔ የሚያየው እናንተን በመግደል ፍትሃዊ ጥያቂያችሁን ማዳፈን ይቻላል በሚል ትርጓሜ ነው።ወያኔ ይህን የተቀደሰ እምነታችሁንና እንዲሁም ቅንነትና ትእግስታችሁን ለእናንተ የሚመጥን ስልጡን ምላሽ ማፈላለጊያ አድርጎ አያየውም። አላየውም።

የትግል ስልት የሚቀየሰው የባላንጣን ማንነት በሚገባ ግምት ውስጥ በማስገባት እንጂ እኛ የምንፈልገው የትግል ስልት ስለሆነ ብቻ መሆን አይችልም ብለን እናምናለን። እኛ በግንቦት 7 ውስጥ የተሰባሰብን አባላት የወያኔን የእብሪት አመጽ ማስቆም የሚቻለው የወያኔ አፈሙዝ ብቻ ሳይሆን የእኛም ጠመንጃ እሳት የሚተፋ እንደሆነ በተግባር በማረጋገጥ ብቻ ነው የሚል ጽኑ እምነት አለን። ምንም አይነት የስልጣኔና የሞራል ማእቀብ ከማይገዛው ወያኔን ከመሰለ እኩይ ሃይል እራስን ከጥቃት መከላከል ብሎም በወያኔ መቃብር ላይ ሰላምና ነጻነት ማስፈን የተፈጥሮና የዜግነት መብታችን ብቻ ሳይሆን የአላህም ፈቃድና ፍላጎት ለመሆኑ ጥርጥር የለንም። በዚህ አጋጣሚ የግንቦት 7 ህዝባዊ ሃይል ለእስልምና ተከታይ ወንድሞቻችንና እህቶቻችን ሆነ ለመላው የኢትዮጵያ ህዝብ የሚያስተላልፈው ጥሪ የሚከተለው ነው። “የወያኔን የእብሪት አመጽ በፍትሃዊና ህዝባዊ አመጽ ለመመከት በያላችሁበት ተደራጁ። የግንቦት 7 ህዝባዊ ሃይልን ተቀላቀሉ። የወያኔን የግፈኛነት እብጠት በህዝባዊና ፍትሃዊ የመሳሪያ አመጽ እናስተንፍስ” የሚል ነው።

ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ!!!!

ሞት የንጹሃን ደም በከንቱ ለሚያፈሱ በሙሉ !!!!

Hiber Radio: በኦሮሚያ አርሲ ዞን የመንግስት ታጣቂዎች የገደሏቸው ሙስሊሞች ቁጥር እየጨመረ ነው

0
0

ጋዜጠኛ ሃብታሙ አሰፋ

ጋዜጠኛ ሃብታሙ አሰፋ

የህብር ሬዲዮ ዕሁድ ሐምሌ 28 ቀን 2005 ፕሮግራም
> ጋዜጠኛ ሳዲቅ አህመድ የወቅቱን በሙስሊሞች ላይ የተደረገው ጭፍጨፋ ሰላማዊ ትግሉን ይገታው እንደሁ ተጠይቆ ከመለሰው (ሙሉውን ያዳምጡት)
>
ከአርባ ምንጭ የሚሊዮኖች ድምጽ ለነጻነት አስተባባሪ ግብረ ሀይል ም/ል ቃል አቀባይ አቶ ሀብታሙ አያሌው ሰልፉን አስመልክቶ ለህብር ከሰጡት ቃለ መጠይቅ የተወሰደ(ሙሉውን ያድምጡ)
ሙጋቤን እውን ሕዝቡ መረጣቸው ወይስ ራሳቸውን ቀቡ? የአፍሪካ አምባገነኖች የስልጣን ጥም ማሳያ የሆኑት ሙጋቤ በሕዝባቸው በጎ ፈቃድ ተመርጠዋል? ተቃዋሚዎች ያልተቀበሉትን የምርጫ ውጤት ተከትሎ አለመረጋጋት ይከሰት ይሆን? (የዙምባብዌን ምርጫ በወቅታዊ ዘገባ ዳሰነዋል)
ሌሎችም ቃለ መጠይቆች አሉን
ዜናዎቻችን
አባይ ወልዱ በቬጋስ ከትግራይ ተወላጆች ጋር ስብሰባ ሊቀመጡ ነው
በኦሮሚያ አርሲ ዞን የመንግስት ታጣቂዎች የገደሏቸው ሙስሊሞች ቁጥር እየጨመረ ነው
ጋዜጠኛ አበበ ገላው በአዘዛዙ የተወሰደውን ጭፍጨፋ ነጻነት ናፋቂ ኢትዮጵያዊ ሁሉ ሊያወግዘው ይገባል ሲል ጥሪ አቀረበ
ኢትዮጵያ ሰራዊቷን ወደ ሱዳን ድንበር አስጠጋች
እርምጃው የግብጽን ወታደራዊ ዛቻ ተከትሎ እንደመጣ ይነገራል
ኬኒያውያን ባለሀብቶች በኢትዮጵያ ያለው ቢሮክራሲ እንዲቆም ጠየቁ
ኤርትራውያን ስደተኞች ከእስራኤል እንዳይጠረዙ ለአገሪቱ ጠቅላይ ሚኒስትር የተማጽኖ ደብዳቤ ላኩ
ከስራ ማቆም አድማ የገቡ የዋይ.ሲ.ኤስ አሽከርካሪዎች የጤና ኢንሹራንሳቸው በኩባንያው ተቋረጠ
ሌሎችም ዜናዎች አሉን

“ዘላቂ ሰላምን ለማስፈን ወያኔን እናስወግድ”–ግንቦት 7

0
0

ginbot 7(ዘ-ሐበሻ) ግንቦት 7 “ዘላቂ ሰላምን ለማስፈን ወያኔን እናስወግድ” ሲል ጥሪውን አቀረበ። ንቅናቄው ለዘ-ሐበሻ በላከው መግለጫው “በአገራችን ሰላም እንዲሰፍን እና መሠረታዊ መብቶቻችን ተከብረውልን መኖር እንድንችል ወያኔን ለማስወገድ ቆርጠን እንነሳ።” ብሏል።
“ወያኔ ወገኖቻችንን እየገደለ፤ አገራችንን እና ሕዝቧን በሽብር እያመሰ ነው። ከአርብ ሐምሌ 26 ቀን 2005 ዓም ጀምሮ በአገራችን የተለያዩ ክፍሎች የወያኔ ሠራዊት ባልታጠቁና ባልተዘጋጁ ሰላማዊ ዜጎች ላይ ጥይት እያዘነበ ይገኛል። እስካሁን የሞቱና የቆሰሉ ሰዎች ቁጥር ማወቅ ቀርቶ መገመት እንኳን አዳጋች ነው። ሞስሊም ወገኖቻችን፣ በሕጋዊ መንገድ ለውጥ እናመጣለን ብለው የሚያምኑ ሰላማዊ ታጋዮች፣ ሕፃናትና አዛውንት የጥቃቱ ሰለባ ናቸው። ” ያለው የግንቦት 7 መግለጫ “የወያኔ ግንባር ቀደም የጥቃት ሰለባዎች ሰላማዊነታቸው ለማሳየት እጆቻቸውን አስረው ፍትህ ሲማፀኑ የነበሩ ዜጎች ናቸው። ሕግ የማያውቀው ወያኔን በሕጋዊ መንገድ ታግለን መሠረታዊ መብቶቻችንን እናስከብራለን ያሉ ወገኖቻችን በግፍ ተግደዋል፤ ተደብድበዋል፤ ተግዘዋል። የምዕራብ አርሲ ከተሞችና መንደሮች በአጋዚ ጦር ተወረዋል። አዲስ አበባም ውስጥ ዋይታ በርክቷል።” ሲል ይተነትናል።
“ግንቦት 7: የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ በወያኔ ፋሽስታዊ እርምጃ ሕይወታቸውን ላጡ ወገኖቻችን ቤተሰቦች ሁሉ የተሰማው መሪር ሀዘን ይገልፃል። እንደዚሁም ለአካል ጉዳት ለተዳረጉ፣ ለተዋከቡ፣ ለተረገጡ፣ ለጅምላ እስር ለተዳረጉ ወገኖቻችን ሁሉ በደረሰባቸው በደል መቆጨቱን ይገልፃል። ” የሚለው ግንቦት 7 ‘ወያኔ በሥልጣን ላይ እስካለ ድረስ የእምነትም ሆነ ሌላ ማናቸውን ነፃነት ሊኖር እንደማይችል የትናትናና የዛሬው ድርጊት አንድ ተጨማሪ ማስረጃ ነው። ወያኔ በሥልጣን መንበር ላይ ውሎ ባደረ መጠን እንዲህ ዓይነቱ መርዶ መስማታችን የማይቀር ነው ብሎ ግንቦት 7 ያምናል። የኢትዮጵያ ሕዝብ መከራ እንዲያበቃ ወያኔ ከሥልጣን መወደግ አለበት፤ ገዳዮች ለፍርድ መቅረብ አለባቸው።” ብሏል።
የንቅናቄው መግለጫ በማጠናቀቂያው ላይም “ግንቦት 7: የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ የሰላማችን ዋስትና የወያኔ መወገድና በምትኩ የሕዝብ ይሁንታ ያገኘ መንግሥት መተካት ነው ብሎ ያምናል። ስለሆነም በአገራችን ሰላም እንዲሰፍን እና መሠረታዊ መብቶቻችን ተከብረውልን መኖር እንድንችል ወያኔን ለማስወገድ ቆርጠን እንነሳ።” ሲል ጥሪውን አቅርቧል።

Viewing all 15006 articles
Browse latest View live