Quantcast
Channel: Ethiopian News | ዘ-ሐበሻ | Latest News Provider | News For All
Viewing all 15006 articles
Browse latest View live

የኤፍሬም ታምሩ አልበም ጥያቄ አስነሳ * ይልማ ገብረአብ 250 ሺህ ብር ይገባኛል አለ

$
0
0

(ዘ-ሐበሻ) ድምፃዊ ኤፍሬም ታምሩ የቀድሞ ዘፈኖቹን በአዲስ መልክ አስተካከሎ ለገበያ እንደሚቀብ በተለያዩ ጊዜያት ሲዘገብ እንከንም እያጋጠመው ሲዘዋወር ቆይቷል:: ለመጨረሻ ጊዜ ይወጣል በተባለበት ሰዓት የእናቱ ከዚህ ዓለም በሞት መለየት አልበሙን አዘግይቶታል::

ውስጥ አዋቂ እንደዘገበው ኤፍሬም በቅርቡ አልበሙን ለመልቀቅ በቤቱ ትልቅ የምስጋና ፓርቲ አዘጋጅቶ ቢጨረስም በዚህ በዓል በኋላ ታዋቂው የዘፈን ግጥም ደራሲ ይልማ ገብረአብ ጥያቄ አንስቷል:: “ከዚህ ቀደም እነዚህን ዘፈን ግጥሞች ለካሴት ሥሰራ የተከፈለኝ በአንድ የዘፈን ግጥም አንድ ሺህ ብር ብቻ ነው:: አሁን ግን በዚህ አዲሱ የአፌሬም አልበም ውስጥ ለተካተቱት 10 ዘፈን ግጥሞቼ ለ እያንዳዳቸው 25 ሺህ ብር ጠይቄያለሁ” ብሏል:: ይህም 250 ሺህ ብር መሆኑ ነው:: ዝርዝሩን ያድምጡ::

Ephrem Tamiru

The post የኤፍሬም ታምሩ አልበም ጥያቄ አስነሳ * ይልማ ገብረአብ 250 ሺህ ብር ይገባኛል አለ appeared first on Zehabesha Amharic.


ጋዜጠኛውን የደበደበው አርቲስት ዳንኤል ተገኝ በፍርድ ቤት ተቀጣ

$
0
0

ከአንዲት ግለሰብ ጋር ፊልም እስራልሻለሁ በሚል ገንዘብ ተቀብሎ ገንዘቡን ክዷል የሚል ክስ ቀርቦበት ፍርድ ቤት እየተመላለሰ የሚገኘው አርቲስት ዳንኤል ተገኝ ለምን ይህን ጉዳይ ዘገባችሁ በሚል የኢትዮፒካ ሊንክ ጋዜጠኞች ላይ ጥቃት ለማድረስ አስቦ በአንዱ አዘጋጅ ላይ ድብደባ በመፈጸሙ በከሰሰበት ክስ ጥፋተኛ ተብሎ 2 ቀን ከታሰረ በኋላ ተፈረደበት:: ዝርዝሩን ያድምጡ::


Daniel tegegne

The post ጋዜጠኛውን የደበደበው አርቲስት ዳንኤል ተገኝ በፍርድ ቤት ተቀጣ appeared first on Zehabesha Amharic.

ዘሚ የኑስ –የኦቲዝሟ «አምባሳደር»

$
0
0

በልጅነት ዕድሜያቸው በደማቸው ውስጥ በሰረፀው የሥነ ውበት (ኮዝሞቶሎጂትምህርት በመታነፅ በሙያው በመካን አገራቸው ላይ በዓይነቱ የመጀመሪያ የሆነ የሥልጠና ማዕከል በመክፈት ከስድስት ሺ በላይ ባለሙያዎችን ማፍራት ችለዋል።

zemi yenusበተጓዳኝም ችግረኛ ወጣት ሴቶችንና በሴተኛ አዳሪነት ለሚተዳደሩ ሴቶች በሚሰጡት ነፃ የትምህርት ዕድል በሥነ ውበት ሙያና የሕይወት ክህሎት ትምህርት እንዲያገኙ በማድረግ ሥራ ፈጥረው ራሳቸውን እንዲረዱና የኢኮኖሚያዊ ነፃነት እንዲቀዳጁ በማድረግ የመልካም ስም ባለቤት ለመሆንም በቅተዋል። 

የውበትን ማራኪነት በመጠቀምና በመገንዘብ በዓይነቱና በይዘቱ የመጀመሪያ የሆነ የብሔር ብሔረሰቦችን አልባሳትንና ባህልን የሚያሳይ ኤግዚቢሽን በማሳየት ለአገራችን አልባሳት የተሐድሶ ዘመን ብርሃን በመፈንጠቅም የዘመን ተሻጋሪ ታሪክ ባለቤት ለመሆን ችለዋል።

በልዩ ልዩ ምክንያት ትዳራቸውን ፈተውና ከቤተሰቦቻቸው ተለይተው ወደ አዲስ አበባ እየፈለሱ የሚመጡ በተለይ ዕድሜያቸው እስከ ሃያ አራት ዓመት የሚሆናቸው ወጣት ሴቶች በችግር ምክንያት ወደ ሴተኛ አዳሪነት እንዳያመሩ የሚያደርግ የባልትና እና የሕይወት ክህሎት የሚቀስሙበት «ስንቅ ቤት» የሚል ፕሮጀክት በመክፍት የወገን አለኝታነትን አትርፈዋል ።

ከሁሉም በላይ እንደ እራሳቸው ልጅ የኦቲዚም ችግር ያለባቸውን ልጆች በልዩ ፕሮግራም በመከታተልና በማስተማር ለተሻለ ህይወት በማዘጋጀት ብቁ ዜጐች እንዲሆኑ የሚረዳ ለመጀመሪያ ጊዜ በአገር አቀፍ ደረጃ «ጆይ የኦውቲስቲክ ልጆች ማዕከል» የተባለ ተቋም መክፈት ችለዋል። በዚህም በአንዳንድ የአዲስ አበባና ኦሮሚያ ክልል ትምህርት ቤቶች ትምህርትና አገልግሎቱን ተደራሽ በማድረግ ህዝባዊ ዕውቅናንና አንቱታን ለማትረፍም በቅተዋል።

በሌላ በኩል በኦቲዝም ምክንያት የችግሩ ገፈት ቀማሽ የሆኑ እናቶችን በማደራጀትና በማሰልጠን የገቢ ማስገኛ ሥራ በመፍጠርና ለተጠቃሚነት በማብቃት ለኦቲስቲክ ልጆች እናቶችም አጋርነታቸውን በተግባር ለማረጋገጥ ችለዋል።

ይህ ብቻ አይደለም በማህበራዊ ጉዳይ ላይ ትኩረት ሰጥቶ ኅብረተሰቡን የሚያወያይና ግንዛቤን የሚያሳድግ «ያገባኛል» የሚል ሳምንታዊ የሬዲዮ ፕሮግራም በፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት በመክፈት በ«ጋዜጠኝነት» ሙያም በመሰለፍ አውቀው በማሳወቅ ላይ ይገኛሉ።

የእነዚህና የሌሎችም ታሪኮች ባለቤት ገና በወጣትነት ዕድሜያቸው በውጭ አገር ተሰደው በልጅነት ዝንባሌያቸው በሥነ ውበት ትምህርት በመሰልጠን ለኮዝሞሎጅስትነት የበቁት በአገራችን የመጀመሪያው የውበት ስራ ሥልጠና ማዕከል ባለቤት እንዲሁም የኒያ ፋውንዴሽን (የጆይ የአውቲስቲክ ልጆች ማዕከልመስራችና ዋና ሥራ አስኪያጅ ወይዘሮ ዘሚ የኑስ ይባላሉ።

የካቴድራሏ ዕምቡጥ

ዛሬ የመልካም ስም ባለቤት ለመሆን የበቁት ወይዘሮ ዘሚ የተወለዱት የዛሬ ሃምሳ አምስት ዓመት በፊት ጥቅምት ቀን 1951 .ም በአዲስ አበባ ከተማ ጣሊያን ሰፈር በሚባለው መንደር ነው። የአቶ አህመድ የኑስና የወይዘሮ ድሐብ ፎሌ አምስተኛ ልጅ የሆኑት የዚያን ጊዜዋ እምቦቅቅላ ህፃን ዘምዘም በካቴድራል ሴቶች ትምህርት ቤት ትምህርታቸውን የጀመሩት ገና በስድስት ዓመታቸው ነበር።

በወቅቱ እንደማንኛውም ተማሪ ትምህርታቸውን በአግባቡና በትጋት የመከታተላቸውን ያህል በተለይ እናታቸው ገና ከልጅነታቸው ጀምሮ ሥራን ባህላቸው አድርገው፣ በሥነ ምግባር ታንፀው እንዲያድጉ በማድረጋቸው በየምዕራፉ ለተሸጋገሩት ዘርፈ ብዙ የሕይወት ጉዞ በእጅጉ እንደጠቀማቸው ይናገራሉ። ከሕፃንነታቸው ጀምሮ ከአደጉበት በቅሎ ቤት አካባቢ እየተመላለሱ ካቴድራል እየተመላለሱ ትምህርታቸውን የተከታተሉት የዜያን ጊዜዋ ሕፃኗ ዘምዘም በዕውቀት እየተኮተኮቱ ከክፍል ክፍል እየተዘዋወሩ በእድሜያቸውም እየደረጁ ሲሄዱ የሥነ ጥበብ (አርትዝንባሌ በውስጣቸው ሰረጸ። ይሁን እንጂ የነበረው ሥርዓተ ትምህርት ከዝንባሌያቸው ጋር ሆድ እና ጀርባ ሆነው ፍጹም ሳይገናኙ እንዲቆዩ አድርጓቸዋል። የስምንተኛ ክፍልን ብሔራዊ ፈተና አልፈው ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ሲገቡ እንኳን በዝንባሌያቸው ለመማር አልቻሉም።

በእርግጥ ዲዛይነሩና ልብስ ሰፊው አባታቸው (ከገጠራማው የአገራችን ክፍል የእረኝነት ሥራቸውን በመተው ከጣሊያኖች ዘንድ ተጠግተው በቀሰሙት ሙያ የታላላቅ ባለሥልጣኖችንና የአምባሳደሮችን ሙሉ ልብስ ዲዛይን አውጥተው በመስፋት እውቅና የአተረፉልጆቻቸውን ለማስተማር ልዩ ትኩረት ነበራቸው። እናም ውሳኔያቸው ልጃቸውን ናዝሬት ትምህርት ቤት ለማስገባት ቢሆንም የዚያን ጊዜዋ ተማሪ ዘምዘም ግን ከጓደኞቻቸው «አልለይም» በማለታቸው የእቴጌ መነን ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪ ይሆናሉ። ይሁን እንጂ ተማሪ ዘምዘም በመማር ማስተማሩ ሂደት የቆዩት ለሦስት ወራት ብቻ ይሆናል። 

ነገሩ እንዲህ ነው፤ በወቅቱ የእቴጌ መነን ትምህርት ቤት የዘጠነኛ ክፍል የአማርኛ ቋንቋ መምህር የነበሩት «ሴቶችን የሚያንቋሽሹና የሚያዋርዱ» ምሳሊያዊ አባባሎችን እንዲነግሯቸው ወይም በጽሑፍ እንዲሰጧቸው ይጠይቋቸዋል። የመምህሩ ዕኩይ ጥያቄ ያናደዳቸውና ያበሳጫቸው ለግላጋዋ ተማሪ ፊት ለፊት ለመቃወም እንደማይችሉ ያምናሉ። ከጓደኞቻቸው ጋር ግን «በያገባኛል» ስሜት ይወያያሉ። ጉዳዩን ለትምህርት ቤቱ ዳይሬክተር ቢከሱም ተደማጩ አስተማሪው ስለሆኑ ውጤቱ ጉንጫ አልፋ መሆኑንም ጓደኛሞቹ ይገባቸዋል። የመምህሩ ፀረእኩልነት አስተሳሰብ ያስቆጣቸው የካቴድራሏ ዕምቡጥ ጉዳዩን ለአባታቸው በመንገር የሚወዱትን የአማርኛ ትምህርት በአግባቡ ይከታተሉ ዘንድ ሌላ ትምህርት ቤት እንዲያስገቧቸው ይጠይቋቸዋል። በልጃቸው መልካም አስተሳሰብ የተስማሙት አባትም በመኖሪያ ቤታቸው አካባቢ በሚገኘው ንፋስ ስልክ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት እንዲገቡ ያደርጓቸዋል። በዚሁ ትምህርት ቤት እስከ አስራ አንደኛ ክፍል ድረስ ትምህርታቸውን በመከታተል ላይ እያሉ ያልጠበቁትና ሕሊናቸው የማይቀበለው ሁኔታ ይከሰታል።

ወቅቱ የአብዮት ጊዜ ስለነበር ወጣቱ በተለይም ተማሪው እንደወንጀኛ ተቆጥሮ በፀረሕዝብነት ተፈረጀ። እናም ተማሪ ዘምዘም በወጣቶች ላይ የሚደርሰው ወከባ አስፈሪ ይሆንባቸዋል። የትምህርት ቤታቸው መዘጋትና መከፈት ያበሳጫቸዋል። ተማሪዎች እየተያዙ ወደ እስር ቤት ሲወሰድ በማየታቸው ስጋት ውስጥ ይገባሉ። ልጃገረዶች ቀበሌ እየተወሰዱ እንደሚደፈሩ ሲሰሙ ደግሞ ይበልጥ በፍርሐት ይርዳሉ። በእርሳቸው ዕድሜ የሚገኙ ተማሪዎች እየተገደሉ መሆኑን ሲሰሙም ሕሊናቸው በሐዘን ይሞላል። በእርግጥ በፖለቲካ እንቅስቃሴ ውስጥ ባይገቡም ተማሪዎች የሚያነሱትን ጥያቄም ያምኑበታል። ነገር ግን ብጥብጡንና የሚያስከተለውን ችግር አይወዱትም። እናም የትግል ምርጫቸው ሰላማዊ ይሆናል። በወጣቱ ላይ ያንዣበበውን ዕልቂት የተገነዘቡት ተማሪ ዘምዘም ወደ ውጭ ሀገር ለመሄድ ታላቅ እህታቸው በፈጠሩላቸው ምቹ ሁኔታ ከሚያፈቅሯቸው እናትና አባታቸው፣ እህትና ወንድሞቻቸው፣ እንዲሁም ከሚወዷት አገራቸው ተለይተው በ1969 .ም ወደ ኢጣሊያ በረሩ። እናም በአስራ ሰባት ዓመት ዕድሜያቸው የስደት ኑሮአቸውን አሀዱ ብለው ይጀምራሉ።

የቤት ሠራተኛዋ 

እነሆ ገና በአስራ አራት ዓመት ዕድሜያቸው ለሴቶች እኩልነትና መብት ተቆርቁረው «በፆታ ዕኩልነት የማያምን መምህር አያስተምረኝም» የሚል የፀና አቋም የያዙት፤ ወጣትነት ወንጀል በሆነበትና የደርግን ጭፍጨፋ በመፍራት ለስደት የተዳረጉት ወጣት ዘምዘም ከኑሮ ጋር ግብግብ ይዘዋል። ፈረንጅ አገር « ዓለም ነው» ሲባል የሰሙት የተጋነነ ወሬ ውሸት ስለመሆኑ ሮም ከተማ ላይ በቀናት ውስጥ እውነታውን ያረጋግጣሉ።

ምንም እንኳ ታላቅ እህታቸው ወደ ጣሊያን እንዲገቡ ምቹ ሁኔታ ቢፈጥሩላቸውም ምግብና መጠለያ እንዲሁም አልባሳትን ለማግኘት የግድ መሥራት እንዳለባቸው ያስገነዝቧቸዋል። እናም ቅምጥሏ የአቶ አህመድና የወይዘሮ ድሀብ ልጅ በምግብ አብሳይነትና በሞግዚትነት ለማገልገል የቤት ሠራተኛ ሆነው ይቀጠራሉ።

አዎ እናታቸው ገና በልጅነታቸው ያስተማሯቸው የባልትና ሙያ፣ ቤት አያያዝና ልጅ አስተዳደግ በእጅጉ ጠቅሟቸዋል። በአጭር ጊዜ ውስጥም የሚሰሩት ምግብ ተወዳጅና ተመራጭ ይሆናል። «እጅሽን ከቁርጥማት ያድነው» አይነት አድናቆታቸውን ይገልጹላቸዋል። በሞግዚትነታቸውም ሩህሩህና ልጅ አፍቃሪ መሆናቸውም በእጅጉ ይወደድላቸዋል። በሌላም በኩል በትርፍ ጊዜአቸው ታይፕ እና አረፍተ ነገርን ወይም ቃላትን በአጭር የመጻፍ (shorthand) ትምህርት መከታተል ይጀምራሉ። 

በቤት ሠራተኛነትና በሞግዚትነት በሚያገኙት ገንዘብ እራሳቸውን በፀሐፊነት ከአሰለጠኑ በኋላ ለአንድ ዓመት ያህል የቆዩበትን ሥራ በማቋረጥ በአንድ የስደተኞች ዕርዳታ ድርጅት ተቀጣሪ ይሆናሉ። በአጭር ጊዜ ውስጥም የፀሐፊነት ሥራቸውን በብቃት ይወጣሉ። በሥራቸው ያሳዩትን ቅልጥፍናና ትጋት የተመለከቱ የድርጅቱ አመራሮችም የድርጅቱን ሥራ በጉዳይ አስፈፃሚ መኮንንነት እንዲሰሩ የደረጃ ዕድገት በመስጠት ከጣሊያኖች እኩል ደመወዝ እንዲከፈላቸው ያደርጋሉ።

በኢጣሊያ ቆይታቸው በተለይ ወደ ሥራ ዓለም ከመግባታቸው በፊት በተለያየ ምክንያት በመጠለያ እጦትና በርሃብ አለንጋ የመመታቱን የስደተኞችን ሕይወት ቀምሰውታል። ከእናታቸው የቀሰሙትን የሥራ ክቡርነት አስተሳሰብ የሕይወት ዘመን መመሪያቸው በማድረግ ከቤት ሠራተኛነት ተነስተው በአሥራ ዘጠኝ ዓመታቸው የዕርዳታ ድርጅቱን ከፍተኛ ኃላፊነት ለመሸከም ይበቃሉ። ይህም በመሆኑ ከጉዳይ አስፈፃሚ መኮንንነት በላይ የድርጅቱን ኃላፊ ወክለው ለመሥራትና አመራር ለመስጠትም ይበቃሉ። 

በሌላም በኩል ሊመረቁ ወራት ሲቀራቸው ቢያቋርጡትም የሆቴል አስተዳደር (ሆቴል ማኔጅመንትትምህርት መከታተል ጀምረው እንደነበር ያስታውሳሉ። የካቴድራሏ እምቡጥ፤ የመነኗ የመብት ተሟጋች ዘምዘም አንፃራዊ በሆነ መልኩ የተደላደለ ኑሮ ቢጅምሩም የእናታቸውን፣ የእህቶቻቸውንና የወንድሞቻቸውን እንዲሁም የአገራቸውን ናፍቆት ለማስታገስ ወደ አገራቸው መመለስ እንዳለባቸው ይወስናሉ። እናም የመሄዳቸውን ጉዳይ ኢጣሊያ ለሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ አሳውቀው አዲስ አበባ ይገባሉ።

ይሁን እንጂ ቤተሰቦቻቸውን ለመጠየቅ አገራቸው የገቡት ስደተኛዋ ወይዘሪት ያላሰቡትና ያላለሙት አስደንጋጭ ችግር ይጋረጥባቸዋል። ቀደም ሲል ፈርተውት የወጡት ደርግ «ኢጣሊያን አገር በምትሠራበት የዕርዳታ ድርጅት ለወንበዴዎች ቪዛ እያዘጋጀት ትሰጣለች» በማለት ፓስፖርታቸውን ይነጥቋቸዋል። ይህም በመሆኑ ፓስፖርት አልባ የሆኑት ወጣት ተወልደው በአደጉበት ከተማ እንኳን እንደልባቸው ለመንቀሳቀስ ይሳናቸዋል። 

ቆፍጣናዋ ወጣት ግን የደርግ ጥርጣሬ መሠረተ ቢስ መሆኑንና ሰላማዊ ሰው መሆናቸውን በማስረዳት ይህንንም ኢጣሊያን አገር የሚገኘውን የኢትዮጵያ ኤምባሲ ጠይቀው እንዲረዱ አቤት ይላሉ። አዎ ኤምባሲውም ዘምዘም ሰላማዊ መሆናቸውን ያረጋግጥና ፓስፖርታቸውን ያገኛሉ። በአዲስ አበባ የመቆያ ጊዜያቸውን በማሳጠር ወደ ሮም ይመለሳሉ። እንደተመለሱም ከኢጣሊያ እርቀው ለመሰደድ ይወስናሉ። «ዘምዘም» የሚለውን መጠሪያ ስማቸውን ቤት ውስጥ ይጠሩበት በነበረው ስማቸው በሕጋዊ መንገድ አስቀይረው «ዘሚ» በሚል አዲስ ስም ወደ አሜሪካን አገር ተሸጋገሩ። ከአምስት ዓመት የሮም ቆይታ በኋላ በሃያ ሁለት ዓመት ዕድሜያቸው አሜሪካን አገር የሎስ አንጀለስ ከተማ ነዋሪ ለመሆን ይበቃሉ።

ኮዝሞቶሎጂስቷ

እነሆ ወጣት ዘሚ የኑስ ዳግም ለስደት ቢዳረጉም የአገረ አሜሪካ የኑሮ ዘይቤ እምብዛም እንግዳ አልሆነባቸውም። የካቴድራል ተማሪ ስለነበሩም የእንግሊዝኛ ቋንቋ ችግር ስላልነበረባቸው ከሕዝቡ ጋር ለመግባባትም አላዳገታቸውም። ከሁሉም በላይ ደግሞ ኢጣሊያን አገር ይሰሩበት በነበረው ድርጅት ተባባሪ በነበረው የካቶሊክ ወጣት ማዕከል በፀሐፊነት እንዲሰሩ ምቹ ሁኔታ ስለተፈጠረላቸው በሥራ ፍለጋም አልተንገላቱም። 

በዚህ ሁኔታ ውስጥ እንዳሉ ከልጅነታቸው ጀምሮ በውስጣቸው ከሰረፀው ዝንባሌያቸው ጋር መገናኘት እንዳለባቸው ይወስናሉ፤ ከራሳቸው ጋርም ትግል ይገጥማሉ። እናም የሥነጥበብ አንዱ የሙያ ዘርፍ በሆነው በሥነውበት ጥበብ መማር እንዳለባቸው ውሳኔ ላይ ይደርሳሉ። ጊዜ ሳይሰጡም የዝንባሌያቸው ባለቤት ወደሚያደርጋቸው የሥነውበት የትምህርት ተቋም በመግባት የሙሉ ጊዜ ተማሪ ይሆናሉ። ፍላጐታቸውን ለማሳካት በፅናትና በትጋት ትምህርቱን በመከታተላቸውም ሦስት ዓመት የሚፈጀውን ትምህርት በአንድ ዓመት በማጠናቀቅ በዲፕሎማ ይመረቃሉ።

የተፈጥሮ ውበት እንዴት እንደሚጠበቅ፣ እንዴትስ መንከባከብ እንደሚገባ፣ የተጐዳውንስ እንዴት ማስተካከልና ማስዋብ እንደሚቻል፣ ስለ ቆዳ እንክብካቤ፣ ስለፀጉር ውበት፣ ስለፀጉር ኬሚካል አጠቃቀም፣ ሳይንሱን በንድፈ ሃሳብ ደረጃ በሚገባ መቅሰም ቻሉ። ተግባራዊ ልምድ ለመጋራት ደግሞ በሎስ አንጀለስ ከተማ ብቻ ሳይሆን በዓለም አቀፍ ደረጃ ታዋቂ ከሆኑና ታላላቅ የውበት ሳሎን ካላቸውና የዘርፉ ሊቃውንት ከሆኑት እነ ዥዋን ዥዋን፤ እነ ጀምስ ጊብሰን፣ እነ ጀምስ ካናርና እና ሪኒ ዘንድ በመቀጠር በሙያው ያላቸውን ዕውቀት ያጐለብታሉ። 

ከውስጣዊ ዝንባሌያቸው ጋር በመገናኘት በተግባራዊ ሥራውም አቅማቸውን ያጐለበቱት የዚያ ጊዜዋ ወጣት በሁለት እግራቸው በሚገባ መቆማቸውን በፅናት በማመን «ኒያና ኢንተርናሽናል» የሚባል የውበት ሳሎን በሎሳንጀለስ ይከፍታሉ። ኒያ» የአረብኛ ቃል ሲሆን «መልካም መንፈስ፣ መልካም ዕቅድ…» የሚል ትርጓሜ አለውለስምንት ሰዎች የሥራ ዕድል ይከፍታሉ። በአጭር ጊዜ ውስጥም የወጣቷ ኢትዮጵያዊት የውበት ሳሎን በርካታ ደንበኞችን ያፈራል፤ ገበያውም ይደራል። ኢኮኖሚያዊ አቅማቸውም ይጐለብታል። 

ከጥረታቸው ተጠቃሚ የሆኑት የሥነውበት ሙያተኛዋ ሥራቸውን የማጠናከራቸውን ያህል በፀጉር ኬሚካል አጠቃቀም፣ በቆዳ እንክብካቤና አያያዝ ላይ የስፔሻላይዜሽን ትምህርታቸውን በመቀጠል ስፔሻሊስት ያደርጋቸውን የምስክር ወረቀት ለመቀበል በቅተዋል። 

ለአሥራ አራት ዓመታት አሜሪካን አገር ሲኖሩ ቤተሰቦቻቸውን ከመርዳት ባይቆጠቡም በተለይ ደርግ ከወደቀ በኋላ አገራቸው በመግባት ከሚወዷት አገራቸውና ከሚያፈቅሯቸው ቤተሰቦቻቸው ጋር ለመገናኘት ብርቱ ፍላጎት ስለነበራቸው ጉዞ ወደ ሀገር ቤት ያደርጋሉ። ጉብኝታቸውን አጠናቀው ወደ አሜሪካ ከመመለሳቸው በፊትም እትብታቸው ወደተቀበረባት አዲስ አበባ በመመለስ በሚችሉት ሁሉ ለአገራቸው ዕድገት አስተዋጽኦ ለማድረግ የፀና አቋምና ውሳኔ ላይ ይደርሳሉ። 

አገራዊ ትሩፋት

አዎ «ሰው ከተሰማራ እንደየስሜቱ በዋለበት ቦታ አይቀርም ማፍራቱ» እንዲሉ ሆነና በልጅነት የሙያ ዝንባሌያቸው በዕውቀት የታነጹትና በኢኮኖሚ አቅማቸው የደረጁት ወይዘሮ ዘሚ የኑስ «ማን እንዳገር» በማለት ከአስራ ዘጠኝ ዓመት በኋላ ጓዛቸውን ጠቅልለው በ1987.ም በሙሉ ፍላጐትና ከልብ በመነጨ ደስታ ወደ አገራቸው ይመለሳሉ። 

ረዘም ያለ ጊዜም ሳይወስዱ የላቀ እውቀትና ዕውቅናን በተቀዳጁበት በሥነውበት (ኮስሜቶሎጂሙያ በአገራችን የመጀመሪያ የሆነውን «ኒያና የውበት ሥራ የሥልጠና ማዕከል» የተባለ ትምህርት ቤት በመክፈት ዘመን ተሻጋሪ ታሪክ ያስመዘግባሉ። ለሰባ አምስት ወገኖቻቸው የሥራ ዕድል ከመክፈታቸው ባለፈም ትምህርት ቤቱን ለጊዜውም ቢሆን እስከአቋረጡበት 2004 .ም ድረስ ከስድስት ሺ በላይ የሥነውበት ባለሙያዎችን ማፍራት ችለዋል። በአስራ ስድስት ዓመት የትምህርት ቤቱ የመማር ማስተማር ሂደት ምንም እንኳን አብዛኛዎቹ ዜጐቻችን ቢሆኑም ከናይጄሪያ፣ ከኬንያ፣ ከዛምቢያ… የመጡ ተማሪዎችንም በሙያው እንዲካኑ አድርገዋል።

«…እኔ ፈጣን ሥራ ፈጣሪ ነኝ፤ የፈጠራ ውጤቱን ተግባራዊ ከአደረጉ በኋላ የሥራ ዕድሉን ሌሎች እንዲቀጥሉበትና እንዲጠቀሙበት እየተውኩ በመውጣት ወደ ሌላ አዲስ የፈጠራ ሥራ ላይ ነው የማተኩረው፤ በአንድ ሥራ ላይ ብዙ ጊዜ ማጥፋት አያስደስተኝም…» የሚሉት የሥነ ውበት ጠቢቧ፤ ይህም በመሆኑ ከኒያና የውበት ሥራ ሥልጠና ማዕከል የተመረቁ ዘጠና በመቶ የሚሆኑት ሠልጣኞቻቸው በቀሰሙት ትምህርት በመጠቀም በዕድገት ጐዳና በመገስገስ ላይ እንደሚገኙ ይናገራሉ። ከሁሉም በላይ የሙያ ልጆቻቸው አገር ውስጥ ብቻ ሳይሆን በሌሎች አገሮች ጭምር የሥነ ውበት ትምህርት ቤት መክፈት መቻላቸው ያስደስታቸዋል። የውበት ሳሎንና ስፓ እንዲሁም የባህል «ጭስ ቤትም» ከፍተዋል። አፍሪካውያን ተመራቂዎቻቸውም በየአገራቸው ውበት ሳሎንና ትምህርት ቤት ለመክፈት በቅተዋል። 

ኒያና የውበት ሥራ ሥልጠና ማዕከል ዓላማው በሙያው ለመሰልጠን የሚፈልጉ ወገኖቻችንን በማብቃት ተጠቃሚ እንደሆኑ ማድረግ የመሆኑን ያህል ለጊዜው ሥልጠናውን ቢያቋርጡትም በአጭር ጊዜ ውስጥ አደረጃጀቱንና ሥርዓተ ትምህርቱንም ከፍ አድርጐ እንደገና የመማር ማስተማሩን ሂደት እንደሚጀምር ይናገራሉ። የሥልጠና ማዕከሉ ተግባራዊ እንቅስቃሴ በአደረገባቸው ዓመታት በተለይ ችግረኛ ወጣት ሴቶችንና በሴተኛ አዳሪነት ለተሰማሩ ወገኖች ነፃ የትምህርት ዕድል በመስጠት ከችግራቸው እንዲላቀቁ በማድረግ የወገን አለኝታነታቸውን አረጋግጠዋል። በተጨማሪም ከሚሰጡት ሙያዊ ሥልጠና ባለፈ ኤች አይ ቪን በመከላከሉ ረገድ አቅማቸው የፈቀደውን ሁሉ አስተዋፅኦ አድርገዋል። እንዲሁም ወቅታዊ በሆኑ አገራዊ ችግሮች ላይም በንቃት በመሣተፍ በጐ ተግባራትን ፈጽመዋል።

ይህ በዚህ እንዳለ የሙያው አፍቃሪዎችን በሥነውበት ሙያ ከማነፅ ባሻገር የውበትን ማራኪነት በመጠቀም «… በአይነቱ የተለየ በአገራችንም የመጀመሪያ የሆነ የብሔር፣ ብሔረሰቦችንና ሕዝቦችን ባህልና አልባሳት የሚያስተዋውቅ አውደ ርዕይ በ1997 .ም አዘጋጅቼ በኤግዚቢሽን ማዕከል በሕዝብ እንዲታይ አደረኩ። ይህን በማድረጌም የአገራችንን አልባሳትና ቱባ ባህል አስተዋወኩ። የሸማ ሥራ ውጤትን ይበልጥ በማስተዋወቅ ሙያው የበለጠ እንዲስፋፋና ተጠቃሚ መሆን እንደሚቻም አመላከትኩ። የአገሪቱንም ገፅታ ለመገንባት ሞከርኩ። የኤግዚቢሽኑን ውጤታማነትም በአጭር ጊዜ ውስጥ የአልባሳትን ተፈላጊነትና ተወዳጅነት ጨምሮ ለመመልከት አስችሎኛል…» የሚሉት የሥነውበት ምሁሯ በሌላም በኩል ኤግዚቢሽኑ ዛሬ እርካታን ለተጐናፀፉበት ታሪካዊ ምዕራፍ እንዳሸጋገራቸው ያስታውሳሉ።

የኦቲዝሟ «አምባሳደር»

በሌላ ህይወታቸው ደግሞ ባለትዳርና የሁለት ልጆች እናት ለመሆን የበቁት ሥራ ፈጣሪዋና ችግር ፈችዋ ወይዘሮ ዘሚ ከአሜሪካ ከመጡ በኋላ ልጃቸው የኦውቲዝም እክል እንዳለበት ያረጋግጣሉ። በዚህ ምክንያት ሕብረተሰቡ ስለኦቲዝም ማወቅ እንዳለበት ያሰባሉ። እናም በተደራጀ መልክ ያንን ማራኪ ኤግዚቢሽን በመጠቀም ለዛ በአለው የአነጋገር ብቃታቸው ስለኦውቲዝም ያወቁትን ያሳውቃሉ። መገናኛ ብዙኃንም የኦውቲዝሟን «አምባሳደር» ተከትለው ስለ ኦውቲዝም አስተጋቡ።

በእርግጥ ወይዘሮ ዘሚ የኑስ የኦቲዝም እክል ያለበትን ልጃቸውን አሜሪካን አገር ማስተማር እንደሚችሉ ያምናሉ። ግን ደግሞ ልጃቸው ከመሰል አቻዎቹ ጋር በአገሩና በወገኑ መካከል እንክብካቤና ትምህርት ማግኘት አለበት የሚል የፀና አቋም ይይዛሉ። ገና አዳጊ ወጣት በነበሩበት ወቅት የደርግን ጭፍጨፋና ሰቆቃ ፈርተው ቢሰደዱም በልጃቸው ምክንያት ዳግም መሰደድ እንደሌለባቸው ይወስናሉ። እናም «…ልዩውንና ፈታኙን የኦቲዝም መጋረጃ በመግለጥ ለምን የብርሃን ጮራ እንዲፈነጥቅ አላደርግም…?» በማለት ወላጆች ለልጆቻቸው ትልቅ ነገር እንደሚመኙላቸው ሁሉ በኦቲዝም ምክንያት ልጅን በእግር ብረት ማሰር ምን ያህል ዘግናኝና ኢሰብአዊ መሆኑን በየአጋጣሚው ማስተማሩን በትጋት ተያያዙት። ጥረታቸው ፍሬ አፍርቶም የሕዝብ ንቅናቄ እንዲፈጠር ያደርጋሉ። መንግሥትም ድጋፉን ቸራቸው። እናም የሥነ ውበት ሥራ ሥልጠናውን እያካሄዱ በነበረበት ወቅት በተጓዳኝ የኦውቲዝምን ጉዳይ ወደ አንድ ታላቅ ታሪካዊ ምዕራፍ ያሸጋግሩታል።

«ጐሽ ለልጇ ስትል ተወጋች» እንዲሉ ሆነና ወይዘሮ ዘሚም አገራዊ አጀንዳቸውን ዕውን ለማድረግ ሰለቸኝና ደከመኝ ሳይሉ እልክ አስጨራሽ ውጣ ውረዶችን በማለፍ «ኒያ ፋውንዴሽን» የሚል ተቋም መሰረቱ። በስሩ በኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን በምሥራቅ አፍሪካም የመጀመሪያው የሆነ «ጆይ የኦውቲስቲክ ልጆች ማዕከል» የተባለ ተቋምም አቋቋሙ። የአያሌ ኦውቲስቲክ ልጆችን የወደፊት ዕጣ ፈንታ የሚለውጥ፤ የእርሳቸው ቢጤ እናቶችን የሕይወት ዘመን ሰቀቀንና ሐዘን የሚቀርፍ ማዕከል በማቋቋም «አበጀሽ» ተባሉ።

እነሆ ማዕከሉ እ..አ በ2002 ከተመሠረተ በኋላ ሥራውን የጀመረው የወይዘሮ ዘሚን ልጅ ጨምሮ በሌሎች ሦስት የኦውቲስቲክ ልጆች ነው። « …የእኔ አስተማሪዎች ልጄና በማዕከሉ የተቀበልኳቸው ሌሎች ሕፃናት ናቸው…» የሚሉት ወይዘሮ ዘሚ የአላቸውን የንባብ ባህል በመጠቀም፤ ጥናትና ምርምርም በማድረግ የማዕከሉን ተቋማዊ አደረጃጀት አሳድገውታል። እነሆ ዛሬ በማዕከሉ የሚገለገሉ የኦውቲስቲክ ልጆች ቁጥር ሰማንያ ደርሷል። «…ኦቲዝም እንከን እንጂ በሽታ ወይም ሕመም አይደለም…» የሚሉት የማዕከሉ መሥራች፤ ለእንከኑ ፈውስ የሚገኘውም የሕክምና መድኃኒት በመውሰድ ሳይሆን ይልቁንም ለልጆቹ ልዩ የትምህርት ዘዴ በመዘርጋትና ተግባራዊ በማድረግ እንዲሁም የተለየ እንክብካቤ በመስጠት እንደሆነ በአፅንኦት ይናገራሉ። ማዕከሉ ልዩ የማስተማር ዘዴና ጨዋታ፣ ከስሜት ሕዋሳት ጋር የሚገናኝ ፊዚዮ ቴራፒ በመጠቀም መፃፍ እንዲለማመዱ የሚያስችሉ ስዕሎችና ቀለማት እንዲለዩ እንዲሁም ዓይን፣ እጅና አዕምሯቸውን አቀናጅተው ስዕል እንዲሰሩ፣ እንዲነጋገሩና እንዲግባቡ መጠነ ሰፊ ጥረት ያደርጋል። ለኦውቲስቲክ ልጆች በሚመች መንገድ በቀላሉ ማንበብና መፃፍ እንዲችሉ የሚያደርግ በአማርኛና በእንግሊዘኛ የሚሰራ አቡጊዳ ፎኔቲክስ በመፍጠር የባለቤትነት ማረጋገጫ በመጠባበቅ ላይም ይገኛሉ። በማዕከሉ ተጠቃሚ የሆኑት የኦውቲስቲክ ልጆች በዚህ ቴክኖሎጂ ማንበብና መፃፍን ፣አንብበው መረዳትና መግባባትን ችለዋል። እየቻሉም ነው።

የወይዘሮ ዘሚ ጥረትና ውጤት በአዲስ አበባ ብቻ ተወስኖ አልቀረም። መንግሥትም የጀመሩትን ጥረት በአገሪቱ ተደራሽ እንዲሆን ድጋፉን አልነፈጋቸውም። እሳቸውም የኦውቲዝም ልጆች መምህራንን ከማሰልጠን ባለፈ በአዲስ አበባ አስር የመንግሥት ትምህርት ቤቶች አንድ አንድ ክፍል በማዘጋጀት የኦውቲስቲክ ልጆች በትምህርት ገበታ ላይ እንዲገኙ አስችለዋል። በኦሮሚያ ክልል በአዲስ አበባ ዙሪያ በሚገኙ አምስት ትምህርት ቤቶችም የኦውቲዝም እክል ያለባቸው ሕፃናት ቀን ወጥቶላቸው የተማሪነትን ወግ አግኝተዋል።

ወይዘሮ ዘሚ ለኦውቲስቲክ ልጆች ብቻ ሳይሆን እንደእርሳቸው ልባቸው ለሚደማ እናቶችም አለኝታ ሆነዋል። በእርግጥ የኦውቲስቲክ ልጆች ማዕከል ተቋቁሞ እክል ያለባቸውን ልጆች ለመንከባከብና ለማስተማር በመብቃታቸው እርካታቸው ወሰን የለውም። ትልቁን ደስታቸው የሚያገኙት ግን የአዲስ አበባ አስተዳደር የሰጣቸውን መሬት ከቦሌ ክፍለ ከተማ ከወረዳ አስር ተቀብለው ዋናውን «የኦውቲዝምና ልዩ የዕድገት ፍላጐት ያላቸው ልጆች ማዕከል» ተገንብቶ የኦውቲስቲክ ልጆች ከአሁኑ የበለጠ ልዩ እንክብካቤና ልዩ የትምህርት ዘዴ ተጠቃሚ ሲሆኑ እንደሆነ ይናገራሉ።

የሕይወት ስንቅ

«…የምችለውን በጐ ነገር ሁሉ ማድረግ ያስደስተኛል» የሚሉት የዘመን ተሻጋሪ ታሪክ ባለቤት የሆኑት ወይዘሮ ዘሚ የኑስ ዛሬ ደግሞ «ጋዜጠኛ» ሆነው «ያገባኛል» የሚል የሬዲዮ ፕሮግራም በፋና ብሮድካሲንግ ኮርፖሬት ሳምንታዊ የሬዲዮ ፕሮግራም ጀምረዋል። በዚህ ፕሮግራም በማህበራዊ ጉዳዮች ላይ የውይይት መድረክ ከፍተው ሰናይ ተግባር በማከናወን ላይ ይገኛሉ።

በሌላም በኩል ለኦቲዝም ጉዳይ የተለየ ትኩረት ሰጥተው የመንቀሳቀሳቸውን ያህል ለኦውቲስቲክ ልጆች እናቶችም በአለኝታነት በመቆም በሥራ ፈጣሪነት ቆመዋል። ለዚህም ልጆቻቸው ጆይ የኦውቲስቲክ የልጆች ማዕከል ቢገቡም ባይገቡም በተናጠልም ሆነ በማደራጀት የገቢ ማስገኛ ሥራዎችን በመፍጠር ተጠቃሚ እንዲሆኑ አስችለዋል።

ይህ በዚህ እንዳለ መካኒሳ አካባቢ «ስንቅ ቤት» የሚል ፕሮጀክት ነድፈው እውን በማድረግ በተለይ ዕድሜያቸው እስከ ሃያ አራት ዓመት ያሉ ወጣት ሴቶች መጠጊያና የሕይወት ክህሎት ዕውቀት ደሀ ሆነው ወደ ሴተኛ አዳሪነት እንዳይገቡ አርአያነት ያለው ተግባር በማከናወን ላይ ይገኛሉ።

ፕሮጀክቱ በተለይ በተለያየ ምክንያት «ወደ አረብ አገር እንሄዳለን» በማለት ትዳራቸውን ትተው ከወላጆቻቸው ተነጥለው እየጠፉ የሚመጡ ወጣት ሴቶች ሥልጠና ከመውሰዳቸው በፊት ወደ ትዳራቸው እና ወደ ቤተሰቦቻቸው ለመመለስ ፈቃደኛ ካልሆኑ በዝንባሌያቸው መሠረት በቤት አያያዝ፣ በምግብ አዘገጃጀት፣ በፅዳት አጠባበቅ፣ በልብስ ንጽህናና በሌሎችም ተያያዥ ሙያዎች ላይ ስልጠና በመስጠት የሕይወት ዘመን ስንቅ እንዲቀስሙ ያደርጋል። እስከ አሁን አንድ መቶ ወጣት ሴቶችን ያሰለጠኑ ሲሆን፤ ወደፊትም አምስት መቶ ወጣት ሴቶችን በማሰልጠን የትም ቦታ የሚጠቅም ትምህርት እንደሚሰጧቸው ይናገራሉ። 

እንደማጠቃለያ

በነባራዊው ዓለም ውስጥ እውን የሆነውን የሕይወት ውጣ ውረድ በፅኑ መንፈሳዊ ጥንካሬ፤ ወሰን በሌለው የሥራ ትጋት፤ ለዝንባሌያቸው ተገዝተው የሥነውበት ምሁር በመሆን ለአያሌ ወገኖቻችን ሙያቸውንና ዕውቀታቸውን ለማካፈል በቅተዋል። በሥራ ፈጣሪነትና በችግር ፈቺነትም ተሰልፈው ስኬታማ ሆነዋል። 

ወይዘሮ ዘሚ የኑስ ዛሬም ሮጠው አልደከሙም፤ ሰርተውም አልታከቱም። የበለጠ ሰብአዊና ሕዝባዊ አገልግሎት ለመስጠት ዛሬም ፅናት ባለው መንፈስ በመንቀሳቀስ ላይ ይገኛሉ። እየሰጡት ያለው አገልግሎት ወገን ተኮር በመሆኑ «ጋን በጠጠር ይደገፋል» እንዲሉ ማንኛውም አቅም ያለው ሰው የሚችለውን ሁሉ ለማድረግ «አለሁልሽ» ሊላቸው ይገባል። ምክንያቱም የበጐ ተግባር ምሳሌ የሆኑት ወይዘሮ ዘሚ የኑስ እየተገበሩት ያለው ሕያው ተግባር የጋራ አገራዊ ጉዳይ ነውና።

The post ዘሚ የኑስ – የኦቲዝሟ «አምባሳደር» appeared first on Zehabesha Amharic.

የወያኔ የመከላከያ ከፍተኛ በጀት

$
0
0

ginbot 7የወያኔ የመከላከያን ከፍተኛ በጀት ለትግራይ ክልል እንደ ተጨማሪ ልዩ በጀት አድርጎ ይጠቀማል፡፡ በሰራዊቱ ውስጥ ዘረኛ መድሎን ይፈጽማል፡፡ የትግራይ ሪፑብሊክ ምስረታ ህልሙንም አልረሳም፡፡

በአሁኑ ጊዜ 85% የሚሆነው የመከላከያ ሠራዊት ከ1990 ዓ.ም ጀምሮ በትግራይ ክልል ሠፍሮ ይገኛል፣ ይህንንም አጋጣሚ
በመጠቀም ፦

  1. ለሠራዊቱ ቀለብ አቅርቦት ያለ ጨራታ ከአዛዧች ጋር በመመሳጣር፣ የትግራይ ሰዎች ብቻ እንዲያቀርቡ ተደርጓል። አቅራቢ ከሆኑትም መሀል አቶ ጉዕሺ፣ ወ/ሮ ዘውዴ ፣ አቶ ስብሀት ፣ ወ/ሮ አዲስ፣ አቶ ገብረስላሴ፣ አቶ ሃጎስ በመባል የታወቁ ሰዎች ይገኙበታል፡፡ ለሰራዊቱ የሚያቀርቡትም አትክልት ፣ በርበሬ፣ የወጥ እህሎችና ሥጋ፣ ዱቄት ፣ ዘይት ወዘተ. መሆኑ ታውቋል። አቅራቢዎቹ የትግራይ ሰዎች አቅርቦቱም ከትግራይ ክልል እንዲገዛ ተደርጓል።
  2. ሰራዊቱ በከፍተኛ ቁጥር ትግራይ ላይ በመስፈሩ ብቻ ምን ያህል የክልሉን የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ እንደጠቀመ አንድ ምሳሌ እንስጥ፡፡ የወያኔ አንድ ወታደር በቀን 8 ዳቦ ይበላል፡፡ ይህም ማለት ወደ መቶ ሽህና ከእዛም በላይ የሚቆጠረው በትግራይ ውስጥ የሰፈረው ሰራዊት በአማካይ በትንሹ በቀን 800000 ዳቦ ያስፈልገዋል ማለት ነው፡፡ በቀን ይህን ያህል ዳቦ የማቅረብ ስራ ብቻ ምን ያህል ኢንቨስትመንት የሚያስፈልገው እንደሆነ መገመት ይቻላል፡፡ ወያኔ ሰራዊቱ በሆዱ እንዳይከፋበት ካለው ፍላጎት ለምግብ ከፍተኛ ወጪ ያደርጋል፡፡ ካዳቦ ውጭም በእዚሁ በትግራይ ክልል ውስጥ ሰራዊቱን መሰረት በማድረግ የሚመረተው የተለያየ የምግብ ውጤትና ሽያጭ በገንዝብ ሲለካ በብዙ መቶ ሚሊዮኖች ብር የሚቆጠር ይሆናል፡፡
  3. ሌሎች ከቀለብ ውጭ በመደበኛ በጀት የሚገዙ አላቂና ቋሚ እቃዎች፣ የኤሌትሪክ ማሽነሪዎች ፣ የጽህፈት ዕቃዎች፣ ማንኛውም የቢሮና የመኖሪያ ቤት መገልገያ ዕቃዎችና የስልጠና መገልገያ ዕቃዎች፣ በሙሉ ከትግራይ ክልል ብቻ እንዲገዙ በመመሪያ ታዟል። ሌላው ቀርቶ ጠቅላላ የመከላከያ ወታደራዊ አገልግሎትና ሌሎች ጨርቃ ጨርቆች በሙሉ፣ ያለ ጨረታ አድዋ ከሚገኘው ከአልሜዳ ጨርቃ ጨርቅ ፋብሪካ ብቻ እንዲገዛ ተወስኖ፣ ተግባራዊ ከሆነ ብዙ አመታት አስቆጥሯል። ይህ ሰራዊት በአመት ሁለት ግዜ የደንብ ልብሱን እንዲቀይር ከወጣው መመሪያ ጋር ተደምሮ እነአልሜዳ ምን ያህል ገንዝብ ከመከላከያ ሚኒስቴር እንደሚዘርፉ ማየት ይቻላል፡፡
  4. በኢትዮ – ኤርትራ ጦርነት ጊዜ የጦርነቱን አጋጣሚ በመጠቀም 50000 (ሃምሳ ሽህ ) የትግራይ ሚሊሻ በጦርነቱ ትሳትፏል፣ ጦርነቱ ከቀጠለም ይዋጋሉ፣ በሚል ምክንያት ሥራ ላይ ሣይገኙ በየቤታቸው ተቀምጠው፣ በመከላከያ የደሞዝ መክፈያ ሰነድ፣ ከሰኔ 1991 ጀምሮ እስከ ሰኔ 1993 ዓ.ም ድረስ በተራ በወታደር ማዕረግ በወር 500.00 (አምስት መቶ ) ብር ተክፍሏቸዋል። ይህ አሰራር መቋረጡን ማወቅ የቻልንበት ማስረጃ የለም፡፡
  5. በግንባር አካባቢ ወታደራዊ ልምምድ ሲደረግ ልምምዱ የገበሬዎች ሰብል አውድሟል፣ የግጦሽ ሳራቸውን ጎድቷል፣ አትክልታቸውን ሰባብሯል፣ በሚል ሰበብ የልተመጣጠነ ከፍተኛ ዋጋ ይከፈላል። ለምሳሌ አዲግራት ደንጎል አካባቢ፣ በሁለት ሄክታር መሬት ላይ የተዘራ ገብስ ላይ ‹‹የተወሰነ የእግረኛ ልምምድ ተደርጎበት ወደመ›› ተብሎ የግብርና ባለሙያዎች መጥተው ‹‹ከ30-40% ምርት ሊቀንስ ይችላል›› ብለው ሄዱ። ለሰዎቹ ግን የተሰጠው የካሳ ክፍያ 780000 (ሰባት መቶ ሰማኒይ ሺ) ብር ነበር። ይህ ገንዝብ ግን በሙሉ በተራው ገበሬ እጅ የገባ ሳይሆን ሰራዊቱን በዋንኛነት የሚቆጣጠሩትን የትግራይ ተወላጅ የሆኑ ከፍተኛ መኮንኖች ኪስ እንዳደለበ ይታወቃል፡፡
  6. ሠራዊቱ በትግራይ ከተሞችና ገጠሮች በብዛት ሰፍሯል። በሠፈረባቸው አካባቢዎች ሁሉ ለመኖሪያ፣ ለቢሮና ለመጋዘኖች፣ ቤቶችን በውድ ዋጋ ተከራይቶ ይጠቀማል። ሰራዊቱ በሚኖርባቸው ቤቶች፣ ካምፖች፣ በሚገለገልባቸው ቢሮዎች ውስጥ ለቤት ሰራተኛነት፣ ለጽዳት ሰራተኛነትና ለሌሎችም ስራዎች የሚቀጠረው የአካባቢው ተወላጅ ቁጥር በትግራይ የስራ አጡን ቁጥር በመቀነስ ትልቅ ሚና አለው፡፡ ሰፊ የስራ መስክ ሆኗል፡፡
  7. ሰራዊቱ በየወሩ ደሞዙን ተቀብሎ መልሶ የሚያወድመው በእዚሁ ክልል ውስጥ ስለሆነ ከሰራዊቱ የመዝናኛ ፍላጎቶች ጋር የተያያዙ ኢንዱስትሪዎች ከፍተኛ ተጠቃሚዎች የሆኑበት ሁኔታ ተፈጥሯል፡፡ እነዚህ ደግሞ በዋንኛነት በወያኔ ወይም በወያኔ አባላት የተያዙ ናቸው፡፡
  8. ወያኔዎች የወታደሩን ነፃ ጉልበት ተጠቅመው ሠራዊቱን በአፈርን ውሃ ዕቀባ፣ በእርሻና በእርከን ሥራ በአረምና በአጨዳ ሥራ ይጠቀሙበታል።
  9. የመከላከያን የኮንስትራክሽን ማሽነሪዎችና ባለሙያዎች ክልሉ እንደፈለገ በነፃ ይጠቀምባቸዋል። ይህንን በመጠቀም በርካታ መንገዳች ተሰርተዋል። ግድቦች ተገንብተዋል።
  10. ዘረኛነትንና አድሎን በተመለከተ ደግሞ የሚከተለው በደል ይፈጸማል። ከሰራዊቱ በተለያዩ ምክንያት የሚቀነሱ፣ በአካል መጉደል ወይም በሌሎች ምክንያቶች ሊሆን ይችላል፣ የሰራዊቱ አባላት መሃከል በዘር ላይ የተመሰረተ አድሎ ይፈጸማል፡፡

ከሌሎች ብሄረሰቦች የመጡ የሰራዊቱ አባላት የሚሰጣቸው ገንዝብ ከሚሰናበቱበት ግንባር ተነስተው ከሚኖሩበት ክልል የማያደርስ ነው፡፡ ለትግራይ ተወላጆች የሰራዊቱ ተቀናሾች ከመከላከያ ሚኒሰቴር በጀት ወጪ እየተደረገ የሚሰጠው ካሳ በአስር ሽዎች ብር የሚቆጠር ብቻ ሳይሆን፣ እነዚህ የሰራዊቱ አባላት በተለያዩ ስራዎች መቀጠል እንዲችሉ የስልጠና የብድር ሌሎችም አስፈላጊ ግብአቶች ይሟሉላቸዋል፡፡ በኢትዮ ኤርትራ ጦርነት ማብቂያ ከሰራዊቱ በተለያዩ ምክንያቶች የተቀነሱ የሌሎች ብሄረሰብ አባላት የተሰጣቸው ገንዝብ በግለሰብ ደረጃ ከ2000 እስከ 3000 ብር የሚደርስ ብቻ ነበር፡፡ ለትግራይ ተወላጆች ግን ከ30 እስከ 40 ሽህ ብር ነበር፡፡ ሌሎቹ ከሰራዊቱ ከተበተኑ በኋላ ምንም አይነት የመቋቋሚ ድጋፍ ያልተደረገላቸው ሲሆን የትግራይ ብሄረሰብ ለሆኑ የሰራዊቱ አባላት ግን የሚደረገው አጠቃላይ የማቋቋሚ ድጋፍ በብዙ ሚሊዮን ብሮች በሚሰላ ሃብት የተደገፈ ነው፡፡ ይህን አሳዛኝ ዘረኛ አድሎ ወያኔ የሚፈጸመው ወያኔ እንደሚለው 70 ሽህ ዜጎች ሳይሆን 98ሽ ዜጎች ትግራይ ምድር ድረስ ተጉዘው መለስ ዜናዊ ‹‹ለወላይታው ምኑ ነው›› ያለውን የአክሱም ሃውልት ምድር ለመከላከል በረገፉበት ዘግናኝ ጦርነት ማግስት ነበር፡፡ እግረ መንገዳችንን በኢትዮ-ኤርትራ ጦርነት ከሞቱት መሃል አብዛኛው አማሮች ሲሆኑ ከስምንት ሽህ በላይ የሚሆኑ የአፋር ተወላጆች በእዚህ ጦርነት ውድ ህይወታቸውን መክፈላቸውን ማወቅ ችለናል፡፡ አጅግ በርካታ የሆኑ የአካል ጉዳተኞችም ያለምንም ድጋፍ በየክልሎቹ ተበትነው፤ በጦርነት የተቆረጠ እግራቸውንና እጃቸውን መለመኛ አድርገው የመከራ ኑሮአቸውን ይገፋሉ፡፡ በሰዎች መታወቂያ ላይ ሳይቀር የዜጎችን ዘር ለመጻፍ ድፍረቱ ያለው አገዛዝና በሆነ ባለሆነ ስለብሄራዊ ተዋጽኦ ዲስኩር መስጠት የሚቀናቸው የወያኔ ባለስልጣናት ለምን በየጦርነቱ አውድማ የሚማግዱተን የህዝብ ቁጥርና የሟቾቹንና የተጎጂዎችን ብሄራዊ ተዋጽኦ ሊነግሩን
እንደማይፈቅዱ ከእዚህ መረጃ መገንዘብ ይቻላል ፡፡

ለማጠቃለል፡ ወያኔ የኢትዮ – ኤርትራ ፍጥቻ እንዲቀጥል የሚያደርገው፣ አብዛኛውን የሃገሪቱን የመከላከያ ሃይል በቀላሉ ሊቆጣጠረው ከሚችልበት አካባቢ ለማስቀመጥ እድል እንደሚሰጠው ስለሚያውቅ ነው፡፡ የኢትዮ-ኤርትራ ፍጥጫ እስከቀጠለ ድረስ የሃገሪቱ መከላከያ ሃይል ቁጥሩም በጀቱም አይቀንስም፡፡ የሚሰፍረውም በትግራይ ውስጥ ይሆናል፡፡ ይሀ ማለት ከአመት አመት የመከላከያ በጀት በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ ከላይ በጠቀስናቸው መንገዶች በትግራይ ክልል የሚደረገውን የልማት ስራ አጋዥ ሆኖ ይቀጥላል፡፡ ይህንን ጠባብ፣ ዘረኛና ዘራፊ የሆነ የወያኔ ቡድን ፍላጎት እስካሟላ ድረስ፣ ኢትዮጵያ ከድህነቷ ጋር የማይመጣጠን ትልቅ የመከላከያ ሃይል ተሸክማ ኖረች አልኖረች ወያኔን አያሳስበውም፡፡ ወያኔ ሌላው የኢትዮ-ኤርትራ ፍጥጫ እንዲቀጥል የሚፈልግበት ምክንያት፣ ወደፊት ወያኔ በተቀረው የኢትዮጵያ ህዝብ ላይ ሊፈጽም ላሰበው ወንጀል የመከላከያ ሃይሉን የጦር መሳሪያዎች በቀላሉ መጠቀሚያ ለማድርግ በሚያመች ቦታ ማከማቸት ስላስቻለው ነው፡፡ ዛሬ የሃገሪቱ የመከላከያ ሃይል፣ አየር ሃይሉ በሙሉ፣ ሜካናይዝድ ብርጌዱ ከነዘመናዊ ታንኮቹና መድፎቹ፣ በሰራዊት ውስጥ አለ የተባለው ሌላ ዘመናዊ መሳሪያ በሙሉ የሚገኘው በትግራይ ክልል ነው፡፡

በወያኔ የፖለቲካ ስሌት ውስጥ የኢትዮጵያ ህዝብ በወያኔ ዘረኛነትና ዘራፊነት ላይ ተንገፍግፎ ከተነሳ ትግራይን ከነሙሉ የሃይል ማመንጫዎቿ፣ በኤፈርት ዘረፋ ከተሰባሰበው ታላቅ የገንዝብ ካፒታል ጋር፣ በኤርትራ ፍጥጫ ስም በክልሏ ወያኔ እንዲከማች ካደረገው የሃገሪቱ ወታደራዊ ድርጅትና ዘመናዊ የተሟላ የጦር መሳሪያ ጋር፣ በዘር አድሎ ላይ በተመሰረተ የሃገር ውስጥና የውጭ ትምህርትና የሙያ ስልጠና ሲሰጣቸው ከኖሩት የጦርና የሲቪል ሙያተኞች ጋር ከኢትዮጵያ ገንጥሎ፣ እነመለስ ዜናዊ የነገሱባት ነጻ የትግራይ ሪፑብሊክ ለማወጅ ይቻላል የሚል ስሌት ጨምሮ እንደሆነ መረዳት ይገባል፡፡ ወያኔ ከሌሎች ብሄርና ብሄረሰብ የመጡትን የሰራዊት አባላት ከትግራይ አባሮ የሃገሪቱን መከላከያ ሃይል ሙሉ በሙሉ ይዞ ያለምንም መከላከያ ሃይልና መሳሪያ ባዶውን የቀረውን የኢትዮጵያ ህዝብ እንዳሻው እያስፈራራና እያሸበረ በነጻይቱ ትግራይ ላይ ተረገጋቶ የመኖር ተለዋጭ እቅድ ያለው ዘረኛ አገዛዝ መሆኑን መላ የኢትዮጵያ ህዝብ በግዜ ማወቅ የሚገባው ጉዳይ ነው፡፡

The post የወያኔ የመከላከያ ከፍተኛ በጀት appeared first on Zehabesha Amharic.

ፈጣን ሩጫ አይሉት ማራቶን –የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ

$
0
0

የተርጓሚው ማስታወሻ

ይህ ጽሁፍ ዘኢኮኖሚስት ከሚያወጣቸው ኁሉ ብናየውና ብንወያይበት ይጠቅማል በሚል አሳብ ተተርጉሞ ቀርቧል።እራሱን ሳንሱር እያደረገ እንደጻፈው ማየት አያስቸግርም። ከዚህ ትርጉም እንደምታዩት ምዕራብ፡ ምስራቁ ህወሀት መሩ መንግስት ተብዬ ላይ ሁሉም ተስፋ መቁረጡን በግልጥ ያሳያል። የቻይና አምባሳዶር እቅጩን ይናገራል።ያፈርጠዋል። እዲያው አበዛችሁት ዓይነት ነው።በቻይና የምጣኔ ሃብት ግንባታው ሊሰራ የቻለው የቻይና ኮሚኒስት ፓርቲ የህዝቡን ድጋፍ ይዞ ነው።ዛሬ ወያኔ ከህዝብ ተገልሎ ፈርቶ አደር ሆኖ እያነከሰ ነው።ህወሀቶች ቻይና መልሳ ካፒታሊዝምን ተማሩ የምትላቸው ከጊዜው ጋር መራመድ የማይችሉ፤መለስ ከሞተ ወዲያ እንኳን የሰራውን ጥፋት ማየት ያልቻሉ ትቷቸው እንደሄደ ተገትረው የቀሩ ጉዶች ናቸው።ዘኢኮኖሚስት ከመለስ ሞት በኋላ በሰላም በመንግስትነት ተሸጋገሩ ይላል ሌላ ሊሆን እንደሚችል ሁሉ።ዛሬ እየሆነ ያለውን፤የምርጫውን ቧልት፤በሰሜን ኢትዮጵያ ወያኔን ስለሚያጫንቀው ሁኔታ አይተነፍስም።ወያኔ ላይ ያንጃበበው ዳመናም አይታየውም ወይም አይቶት አይናገርም።ለኛ ገሀድ የሆነውን።

የውጭ ተንታኝ ይሳሳታል።እኛ ወያኔ ይወድቃል ህዝብ ተመሯል አይሰነብትም ስንል።በኢትዮጵያ ወያኔን ቀጣይ አድርጎ ያያል። ወያኔዎች ዙሪያው ገደል ሆኖባቸው፤እርስ በርስ እየተወነጃጀሉ ለመሆናቸው ምልክቶች እየታዩ ነው። ወያኔ ዳሩ እየላላበት ነው። መሃሉም ረመጥ እሳት ይሆንበታል። በመጣበት ዘዴ ሊሸኝ። ትርጉሙ እነሆ።

ቢላል አበጋዝ ዋሽንግተን ዲሲ
merkato

ይህ ጽሁፍ ዘ ኢኮኖሚስት May 30th 2015 ያወጣው ጽሁፍ ትርጉም ነው።

ከመላው አፍሪካ በሙሉ እንደ ኢትዮጵያ አድርጎ ቻይና እንደ መራሄ ኮከብ፤ዋና ምሳሌ ተደርጋ የምትወሰድበት የለም።ይሄው ኢትዮጵያ በሜይ 24 እዚህ ግባ የማይባል ውጤቱ ቀድሞ የታወቀ፤ምርጫ አካሂዳለች።ያው ለነባሩ ፓርቲ አዲስ አገዛዝ ዘመን የሚለግስ።ከአሃጉሩ በህዝብ ብዛት ሁለተኛ፤በፍጥነት ታዳጊ ኢኮኖሚ ያላት ኢትዮጵያ ከኮሚኒስት ቻይና ጋር የጠበቀ የአስተሳሰብ ዝምድና አላት።የኢትዮጵያም ባለስልጣናቶችዋን ወደ ቻይና የፓርቲ ትምርት ቤት ትልካለች።ኢትዮጵያኑ በቻይና ኢንዱስትሪ የማስፋፋትን ወንጌልን፤እንዲዋሀዱና ጠንካራ ማከላዊ የማያላውስ ጨቌኝ መንግስትን ባለብዙ ዘውጎች ያውም ያለመስማማትም ታሪክ ያላቸላቸው ህዝቦችን ስለመግዛት፡ያጠናሉ።

ዛሬ ከቻይና ጋር ሁሉም አልጋባልጋ አይደለም። አዲሱ የቻይና አምባሳዶር ያለፈው ፌብሩአሪ አዲስ አበባ ሲደርሱ ለወዳጆቻቸው ያልታሰበ አጉል መልዕክት አድርሰዋል። አምባሳደር ሊ ፋን በዝግ ችሎት የወያኔን ባለስልጣናትን ያለፈው ብቸኝነትን ትታችሁ፤ኢኮኖሚያችሁን ለውድድር ክፈቱት ብለዋል።ንዋይም ዜናም በማዕቀብ መያዙን እያመልከቱ።ባንክና ቴሌ አሰራራቸው የዘመነ ሎጥ ነው።ነጋዴዎች ተመረዋል።ንግድ ወደ ኋላ ቀርቷል።ላመታት ወያኔን ሲያመሰግኑ የኖሩት ቻይኖች ዛሬ ልክ እንደምእራብያውያን ተችዎች ሁሉ ያማርራሉ።

graph

[ሰንጠረጁ የሚያሳየው የኢትዮጵያን በኢንተርኔትና ቴሌ እጅግ ኋላ መቅረትን ነው።]እአአ 2013 የተቀናበረ ሪፖርት የተወሰደ ከመቶ ሰዎች ምን ያህሉ ግለጋሎት ያገኛሉ በሚል የተጠና።

___________________

የችግሩ መሰረት ድፍረት የለም።በኢትዮጵያ መንግስት ውስጥ ያሉ፤የገዥው ፓርቲ አባላት የጸጥታ ተቋሙን የሚቆጣጠሩትም መሻሻሎችን ማድረግ ብቻ የኢኮኖሚ እድገትና የፖለቲካ መረጋጋትን እንደሚያመጡ ያምናሉ። ሊተገብሩአቸው ግን ቀርፋፎች ናቸው።

የመንግስቱ ቀዳማይ ፍላጎት ኢንዱስትሪን ማስፋፋት ነው።ነገር ግን ነጋዴዎች በቢሮክራሲ ተተብትበው ከንዋይም ማንቀሳቀስ ታግተዋል።ባለስልጣናት ሁዋጅያንን ያመለክታሉ።ሁዋጅያንን የቻይና በኢትዮጵያ የጫማ ፋብሪካ ነው።በጥቂት አመታት የሰራተኛን ቁጥርን ከ600 መቶ ወደ 3 ሺ 600 ያደረሰ ነው።ኢትዮጵያ ታዲያ መቶዎች ሁዋጅያንን ትፈልጋለች። ኢንዱስትሪ ሳይስፋፋ 80 % ግብርናን ከማሻሻል በኋላ የሚተርፈውን የሰው ሀይል የምታደርስበት መኖር አለበት።

መንግስት ኢንዱስትሪ መስፋፋትን ለመርዳት መንገጎች ይሰራል፤ባቡር ሃዲዶች ይዘረጋል፤የሀይል ማመንጭያ ጣቢያዎችን፤ግድቦችን ልክ ቻይና እዳረገችው ቅጅውን ይተገብራል።እኒህ ተግባሮች በኦፊሴል የሚታወቀውን የአስር እጅ የኢኮኖሚ ዕድገት አስከትለዋል።ምንም እንኳ ዕድገቱ ሰባትና ስምንት እጅ ነው ተብሎ በውጭ ጠበብት ቢነገርም።የዋጋ ግሽበት ወደ አንድ አሃዝ ወርዷል።ሆኖም ባለፉት ሶስት ዓመታት የዓለም የንግድ ድርጅቶችን ለመቀላቀል የሚደረግ ጥረት የለም።ስራ የሚያንቀሳቅስ የውጭ ካፒታል መገኘቱ አስተማማኝ አይደለም።

ያለው መንግስት ቁንጮዎች መንግስታችን ይገለበጣል የሚል ስጋት ለውጦችን ከመግፋት ችላ እንዲሉ አድርጓል።በአንድ በኩል ሲያስቡት የመልካም ውጤታቸው ሰለባ የሆኑ ይመስላል።ዲሲፕሊንና አስተዳደራዊ ረቂቅነት ላለው መንግስት ቁንጮዎች መጨቆኛ መሳሪያዎችን በጃቸው እንዲሆኑ አድርጓል።ይህ ደግሞ በአሃጉሪቱ ያሉ መሰል ጨቋኞቸ ሊመኙት ብቻ የሚችሉት ነወ። አሁን ያለው መንግስት ቁንጮዎች ካልዘረጉት የጭቆና መረብ ተለይተው ለመኖር አይታሰባቸውም።

ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ከ1974 እስከ 1991 እአአ ከነበረው የስበስ ጦርነት በኋላ አገሪቱን ያደሳት መሃንዲስ በ2012 እአአ ከሞተ ወዲህ ሁኔታው እየባሰ መጣ እንጄ የተሻለ ነገር አልሆነም።መለስ በባህሪው ብርታት፤የአእምሮ ችሎታውና በጦርነት ጊዜ ባፈራቸው ጥብቅ ወዳጅነቶች መሰረት የመንግስቱን ወደፊት እንዲሄድ ያደርገው ነበር።እርግጥ ነው የንግዱ ክፍልና ህዝባዊ ድርጅቶችን ይጠላ ነበር።ቢያስ ግን ጋሬጣ የሆኑ ጉዳዮችን ያስወግድ ነበር።ከሞቱ በኋላ መንግስቱ በሰላም ሽግግር አድርጓል።ረዳትጠ/ሚኒስትሩ እንደታቀደው ስልጣን ይዟል።

አሁን ያለው አመራር የስብስብ ነው።አዲሱ ረዳትጠ/ሚኒስትር መለስ አይደለም።መለስ አንዱ መታሰቢያው የተከፋፈለውን ድርጅት መከፋፈሉን መደበቅ ነበር። ዛሬ ሚኒስትሮች ውሳኔ ከማድረግ በፊት የነባር አመራርን ፈቃድ ማግኘት አለባቸው።የትግራይ ተወላጆች መለስ ወገናቸው የሆኑት ጦሩን፤ጸጥታውን፤ ቴሌን፤የውጭ ጉዳይን ይቆጣጠራሉ።እነርሱ ጡረታ እስቲወጡ ወይ እስቲሞቱ ቢያንስ ሌላ አስር ዓመት ይፈጅ ይሆናል።

አዲሱ ጠ/ሚኒስቴር ለውጥ የሚሻ፤ምክንያታዊ ሰው ነው።በአንጻሩ ደካማ ነው።በመጭው ሴፕቴምበር በኢህአዴግ ጉባኤ የፓርቲው መሪነት እንደገና ይጸድቅለት ይሆናል።ግን መሰንበቱ የተረጋገጠ አይደለም።መለስ ለምን እንዳጨው የረሱት ጥቂቶ ናቸው።ከተበታተነው ደቡብ የአገሪቱ ክፍል በመሆኑ ዋናዎቹን ቡድኖች የማይቀናቀን በመሆኑ ነው።
merera 3
በኢትዮጵያ የሚገኘው የቻይና ህብረተ ሰብ ከፍተኛ አባል ተስፋ በመቁረጥ የአገሪቱ[ኢትዮጵያ] ትልቁ ችግር በቻይና ማእከላዊው መንግስት የክልሎች የበላይ ነው።በኢትዮጵያ ግን ሁሉም ነገር ፌዴራል ነው።የንግድ ቀዬዎች የሚገነቡት በጥናት በተመረጡ ቦታዎች ሳይሆን በኮታ ነው።ከዚህም በላይ እንደ ማኦ መርህ “ፓርቲው ጠመንጃውን ይቆጣጠራል” የሚለው ተረስቷል።ጸጥታ ጠባቂዎቹ ህጉን ራሱን ሆነዋል።

በመጨረሻም የኢትዮጵያ ከፍተኛ መሪዎች ችሎታ ቢኖራቸውም እንደቻይና ችሎታ ያላቸው የመካከለኛ ደረጃ አስተዳዳሪዎች የላቸውም።ባጠቃላይ ብዙ ቻይኖች ኢትዮጵያ በብዙ በየቦታው ባሉ ጉልበተኞች እደተያዘች ያያሉ።

ቻይኖች የማይተነፍሱት መእራባውያን ግን የሚናገሩት የፖለቲካ ስርዓቱ የሚያደርሰው ጭቆና እንዳዳከመው ነው። ወጣቶች ተቆጥተዋል።ስራ አላገኙም።የብሶት መወጫቸው፤መተንፈሻቸው ቶሎ ተዘግቷል። አስተዋይ የተቃዋሚ መሪዎች ለስደት፡ለእስራት ይዳረላሉ።ይህ ደግሞ ለአክራሪዎች ቦታውን ክፍት ያደርጋል። የዩኒቨርሲቲ ቁጥሮች በርከቷል ግን ለብሩሃኑ ተመራቂዎች የተዘጋጀ ስራ የለም።

ፈርቶ አደርሮች ምክንያት ኢትዮጵያ አጣብቂኝ ውስጥ ትገኛለች።ባላት አስደናቂ እድገት የተነሳ ለጥቂት ጊዜ አንከስ እያለችትሄድ ይሆናል።የሀይል ማመንጫዎችዋም ተጨማሪ ድጋፍ ይሰጥዋት ይሆናል። ኢትዮጵያ ቀርቶባታል መሆን ትችል የነበረውን አስደናቂ መሆን አልሆነችም።

http://www.economist.com/news/middle-east-and-africa/21652307-africas-most-impressive-economic-managers-suffer-excessive-caution-neither

The post ፈጣን ሩጫ አይሉት ማራቶን – የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ appeared first on Zehabesha Amharic.

ምርጫ 2007 እና የእስቴት ዲፓርትመንት የፖሊሲ ዉዝዋዜ –የሳዲቅ አህመድ ምርጥ ትንታኔ

ሀገራዊ (ብሔራዊ) ዕርቅ በኢትዮጵያ

$
0
0

አሸብር ሺፈራው ከጀርመን

ከወዲሁ፤- ሀገራዊ ዕርቅ በኢትዮጵያ ስል ሌላ ምንም ሳይሆን፤ ከዘረኛው የትግራይ ሕዝብ ነጻነት ግንባር (TPLF) የባርነት አገዛዝ ነጻ ወጥታ በምትመሰረተው ዴሞክራሲያዊት ኢትዮጵያ ማለቴ መሆኑን ግንዛቤ እንዲያዝልኝ አሳስባለሁ። ብሎም፤
Hand Shake
1ኛ/ ስለ ሀገራዊ ዕርቅ አስፈላጊነት፤-
ሀገራዊ እርቅ በኢትዮጵያ አስፈላጊ ብቻ ተብሎ የሚቀመጥ ሳይሆን፤ በምንም ዓይነት መታለፍ የሌለበት ሂደት ነው የሚል የፈረጠመ አቋም ነው ያለኝ። እንበልና ዛሬም ሆነ ነገ ያገር ቤቶቹ ሰላማዊ ታጋዮች እንደሚሉትም በምርጫ ውድድርም ባይሆን፤ በምርጫ ትግል ስርአቱ ተወገደ ቢባልና፤ ዛሬ በዚህ አረመኔ አጋዛዝ ታፍኖ የተያዘው የሕዝብ ነጻነት ዕውን ቢሆን ብለን ብናልምምና፤ ሕልሙ ተፈጻሚ ሆነ ብንልም እንኳን፤ የተመረጠው መንግሥት ቅድሚያ ሰጥቶ ሊያከናውናቸው ከሚገቡ ዋና-ዋና ጉዳዮች አንዱ ይህንኑ የሃገራዊ ዕርቅ ሂደት ማስጀመር መሆኑን ከወዲሁ ተረድቶ፤ በዚህ አቅጣጫ አፋጣኝ እርምጃ ሳይወስድ፤ የተመረጥኩ መንግሥት ነኝ በማለት ብቻ ሕብረተ-ሰቡ እንደ አንድ ሕዝብ ሆኖ ለዴሞክራሲያዊ ድሎቹ አለመቀልበስ በጋራ እንዲቆም፤ ለሰላም፤ ለልማትና ለብልጽግና ተባብሮ እንዲሰራ ለማድረግ የሚደረገው ጥረት በብዙ ውስብስብ ችግሮች እንደሚደናቀፍ መጠራጠር አይቻልም። ለምን የሚለው ጥያቄ ባይከተል ሃሳቤ የአንባቢን ቀልብ አልሳበም ማለት ነው። መከተሉ ግን የግድ ነው። እናም መልሱ፤

2ኛ/ የዘረኛው የትግራይ ሕዝብ ነጻነት ግንባር (TPLF) አካሄድ፤- ከ24 ዓመት በፊት የስልጣን ኮርቻው ላይ ከተፈናጠጠ ጀምሮ፤ ይህቺን የስልጣን ኮርጫ እስከወዲያኛው አስጠብቆ ለማቆየት፤ ኢትየጵያንና ሕዝቧን ማለቂያ በሌለው የደም ዋጋ ክፍያ ባሪያ አድርጎ ለመግዛት የሚያስችሉትን፤ በተጠናና በከፍተኛ ስሌት የወሰዳቸውን ህዝብን ከህዝብ የሚያናቁሩ፤ መተማመንን የሚያሳጡ፤ ከዜግነት ይልቅ ጎሰኝነትን/ነገዳዊነትን/ጎጠኝነትን እያራገበ፤ ዛሬ ያንዱ ሃይማኖት ተቆረቋሪ ነገ የሌላው አጫፋሪ በመሆን፤ ባጠቃላይ አንዱ በሌላው ላይ እንዲነሳ በማድረግ በፈጸማቸው አጥፊ ተግባራቱ በደረሱ በደሎች፤ በሕብረተሰቡ ውስጥ የታያዙ ቂምና በቀሎች ጋን ሞልተው የፈሰሱ ናቸው። ስለ ትግራይ ሕዝብ ነጻነት ግንባር የዘረኝነት አጀማመር ቀደም ሲል ገና በትግል ዘመኑ በአንድ ጎሳ ላይ ያነጣጠረ ድንፋታውን ትተነው፤ በሥልጣን ዘመኑ መጀመሪያ ላይ ያካሄዳውንና ብዙ ሰው ልብ ያላለውን በማመላከት ትንሽ ብሄድበት ጥሩ ስለመሰለኝ፤ የሚከተለውን ላስታውስ፤

ሥልጣን እንደጨበጠ ወዲያውኑ ጊዜ ሳያጠፋ ያደረገው፤- ጉራጌ ክፍለ-ሃገር ተመድቦ የነበረ የመንግሥት ሰራተኛ ኦሮሞ በመሆኑ ጉራጌ አገር መስራት እንደማይገባው ተደርጎ ወዳኦሮሞው ክፈለ-አገር እንዲሄድ፤ አማራውም፤ ትግሬውም፤ ወላይታውም፤ ሲዳማውም … ወዘተ በዚሁ መልክ እንዲፈናቀል ሲደረግ፤ ለምሳሌ አማራ ክፍለ-ሃገር ለስራ የሄደው ወላይታ ያገባት አማራ ሚስቱ እነደሱው ተመሳሳኝ ሰራተኛ ብትሆን፤ ወላይታ ሄዳ መስራት ስለማትችል፤ ለስራዋ ብላ ከባሏ ተለይታ መቅረት፤ ወይም ባሏን ተከትላ ሄዳ የቤት እመቤት ሆና መቀመጥ ምራጫዋ ሆኖ ነበር። ለወንዱም ይኸው ዕድል ደርሶታል። በዚህ ብዙዎች ልብ ባላሉትና ያሉትም ቢኖሩና በጊዜውም „ethnic cleansing à la eprdf“ በማለት ቢያመላክቱም አዳማጭ ባላገኙበት መጥፎ ሒደት የብዙዎች ትዳር ፈርሷል፤ ቤተሰብ ተበትኗል።

ደጋፊ አጋጣሚ፤- አንዲት ያንድ ጎሳ አባል የሆነች ወጣትና አንድ የሌላ ጎሳ አባል የሆነ ወጣት በውጭ ሃገር ባንድ ከተማ ውስጥ ትምህርታቸውን ሲከታተሉ በነበረበት ጊዜ ተዋውቀው የጋብቻ ሥነ-ሥርዓታቸውን የፈጸሙት ከላይ ያመላከትኳችሁ ዓይነት:-

በኢትዮጵያ ውስጥ የተጀመረው ዘር ማጽዳት ከመጀመሩ 10 ሳምንት ቀደም ብሎ ስለነበርና በዚህ ጊዜ ውስጥም ትምህርታቸውን ጨርሰው ወዳገራቸው መመለሻቸው ስለነበር፤ አውሮፕላን ጣቢያ ስሸኛቸው ወጣቱ „ይህንን ሁኔታ ቀደም ብለን ብናውቅ ኖሮ ጋብቻ አንፈጽምም ነበር። አሁን እኮ እንግዲህ እዚያ ሄደን መለያየታችን ነው። ያሳዝናል!“ ብሎ ጭንቀቱን ሲገልጽልኝ፤ እኔም ጭንቀቱን በማየት፤ ታዲያ ለምን እዚሁ አትቀሩም እንደማንኛውም ሰው ስደት መግባት ነው ስለው፤ እሱማ አይሆንም እዚያው ገብቼ የሆነውን ማየት ነው ብሎ መለያየታችን ትዝ ይለኛል። ከዚህ ጀምራችሁ ወደላይ ዘልቃችሁ አኝዋክ በአኝዋክነቱ፤ አማራው በአማራነቱ የተፈጸመበትን እያከላችሁ የማየቱን ጉዳይ ለአንባቢዎች ልተወውና፤ ባጠቃላይም የዘረኝነት ዋና መገለጫው በሆነው አድሏዊነት ባሕርዩ በፈጸመውና በመፈጸም ላይ ባለው፤ በሹመቱ፤ በሽልማቱ፤ ሃብት በማካበቱ … ወዘተ ያለውን ልዘርዝር ካልኩ ቀኑ መሽቶ ይነጋልና ለቅምሻ ያህል ይህንን ካልኩ በሁዋላ፤

3ኛ/ በቁጥር 2 የተጠቃቀሱትና የሌሎችም መሰል ሂደቶች ዕድል፤- ሂደቶቹ በሕዝብ መሃከል የፈጠሩትን የኑሮ መመሰቃቀል ተከትሎ ከላይ እንዳልኩት ጋኑን ሞልተው የፈሰሱት ቂምና በቀሎች፤ ከባርነት አገዛዙ ማክተም በሁዋላ በምትፈጠረው ደሞክራሲያዊት እትዮጵያ ሽረት ሊያገኙ የሚችሉት አስር ጊዜ ከበረዶ በነጣ ነጻ ፍርድ ቤት በሚሰየሙ ዳኞች ሳይሆን፤ በሃገራዊ ዕርቅ ብቻ ነው። ሃገራዊ እርቅ የፍርድ ቤት ክርክር አይደለም፤ በአስከፊው ስርዓት ውስጥ የሚያልፍ ሕብረተ-ሰብ መሃል አንድ ወገን በዳይ፤ ሌላው ተበዳይ ብቻ ሆኖ ፈጥጦ የሚታይበት ገጽታ የለውም። በዳዩ ተበዳይ፤ ተበዳዩ በዳይ ሆነው የሚፈተሹበትም ሂደት ነው። ሃገራዊ እርቅ ሕብረተሰቡን እንዳለ የሚመለከት ጉዳይ ነው። ሀገራዊ እርቅ ወንጀለኛ ከወንጀሉ የሚነጻበት፤ ከቅጣት የሚያመልጥበት፤ አይደለም። በማንኛም ደረጃና በማንኛውም ጉዳይ ቢሆን፤ በተበዳደሉ ወገኖች መካከል በማንም፤ በምንም ሳይገደዱ፤ ለተፈጸመ በደል እያንዳንዱ ተሳታፊ ተጸጽቶ፤ ከራሱ ጋር ታርቆ፤ ከተበዳዩ ወገን የበቀል ልብን አዘግቶ፤ የይቅር ባይነትን ልብ ለማስከፈት የሚማጸንበት በጎ መንገድ ነው። ተበዳይም ቢሆን፤ ለተፈጸመው በደል የኔስ አስተዋጽኦ ይኖርበት ይሆን? በማለት እራሱን ጠይቆ እንደደረሰበት ሁኔታ እኔም እኮ እንዲህ ባላደርግ ኖሮ ምናልባትም ያ ነገር ተካሮ እዚህ ባልደረሰ ነበር በሚል እራሱን በራሱ የሚወቅስበትም አጋጣሚ ነው።

4ኛ/ የሃገራዊ የእርቁ ቦታ ዩዳይ፤- ሃገራዊ እርቁ የሚደረገው አሜሪካ፤ አውሮፓ፤ አውስትራልያ፤ እስያ ሳይሆን፤ በኢትዮጵያ ምድር ላይ ብቻ ነው። የእርቁም ባለቤት፤ ታራቂውም፤ አስታራቂውም የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው። ያ ሕዝብ ደግሞ ያለው ኢትዮጵያ ውስጥ ነው። ታዲያ በዚያች ምድር ላይ ስለዚህ ዓይነቱ የሃገራዊ ዕርቅ ሂደት ለማሰብ፤ ቢያንስ በመጀመሪያ ደረጃ ከትንሹ እንጀምር ብንል እንኳን፤ በአንድ ላምስት ተጠርንፎ የተያዘው ሕዝብ ከጥርነፋው ተላቅቆ፤ በነጻ የማሰብ መብቱ ታውቆለት፤ ባጠቃላይም ሕዝቡ ከፍርሃት ተላቆ፤ አዩኝ አላዩኝ ሳይል እርስ በርሱ መነጋገር የሚችልበት ሁኔታ መፈጠር ይኖርበታል። አንጻራዊ የሆነም እንኳን ቢሆን፤ ዴሞክራሲያዊ ሁኔታ መፈጠር ይኖርበታል። ይህንን ሁኔታ ለመፍጠር ያለው አማራጭ ደግሞ አንድና አንድ ብቻ ነው። በመጀመሪያ የባርነቱ አገዛዝ መወገድ ነው።! እዚህ ላይ አንድ አለመግባባት እንዳይፈጠር ያስፈልጋል፤ የትግሬ ሕዝብ ነጻነት ግንባር የዘረጋው የባርነት አገዛዝ ተወገደ ማለት፤ በዚህ ድርጅት ስር የተሰባሰቡ ኢትዮጵያውያን ትግሬዎች በዴሞክራሲያዊ መርህ

በምትቆመው እትዮጵያ ውስጥ ህልውናቸው ያከትማል፤ ይጠፋሉ የሚል ቅዠት የሚያስተናግድ ህሊና ካለ፤ ስለ ሃገራዊ ዕርቅ የሚያወራው በደመ ነፍሱ መሆኑን ማጤን ይኖርበታል። ዴሞክራሲያይቱ ኢትዮጵያ የሁሉም ነች። ዴሞክራሲያዊት ኢትዮጵያ የዜጎቿ ሁሉ ነች። ዜጎቿ ደግሞ ደጋጎቹ ብቻ ሳይሆኑ ክፉዎቹም ጭምር ናቸው። የትግሬ ሕዝብ ነጻነት ግንባርም እንደድርጅት ከነዓይኑ ከነጥርሱ ሊቀጥል የማይችልበት ምንም ምክንያት አይኖርም። የሚፈለግበት የዴሞክራሲያዊ ስርዓቱን መተዳደሪያ ደንብ ማክበር ብቻ ነው። የትግሬ ሕዝብ ነጻነት ግንባር የዘረጋው የባርነት ሥርዓት ሲደመሰስ የዚያ ሥርዓት ባለቤትነቱ ያከትማል። ይህ የማይቀር ነው። ከዚህ የሚጨመርም የሚቀነስም ነገር አይኖርም። ከባርነት ነጻ መውጣት በሁዋላ ስለሚደረግ አገራዊ እርቅ ጉዳይ እስከዚሕ ያልኩት ማለት የሚገባኝን ነው ባልልም ከሞላ ጎደል የሆነውን ያህል ያልኩ ይመስለኛል፤ በዚህ ልቋጨውና ወደሌላ ነጥብ ልሻገር፤
5ኛ/ የዚህ የአገራዊ ዕርቅ ጥያቄ ባሁኑ ጊዜ ስለመነሳቱ፤- ዛሬም አንተ እንደምትለው የባርነቱ አገዛዝ ሰፍኖ ባለበት ሁኔታም እየተነሳ ነው፤ ፋይዳው ምንድን ነው? የሚል ጥያቄ መነሳቱ ስለማይቀር፤ በዚህም ያለኝን ሃሳብ ማሳወቁ አስፈላጊ ስለሆነ፤ ዛሬ የሃገራዊ እርቅ ጥያቄ መነሳት ይችላል ማለት ብቻ ሳይሆን፤ መነሳቱ ጠቃሚም ነው የሚል መነሻ ጨብጨ የሚከተለውን አስቀምጫለሁ::

ባሁኑ ጊዜ ይህ የአገራዊ ዕርቅ ጥያቄ የሚነሳው ስለጽንሰ ሃሳቡ ግንዛቤ ለማስገኘት፤ ብሎም በሃገራችን ሁኔታ አስፈላጊ ወይም አላስፈላጊ ስለመሆኑ፤ እንዴትና መቼ፤ የት መደረግ እንዳለበት፤ ጽንሰ ሃሳቡ ቀደም ባሉ ጊዜያቶች ስራ ላይ በዋለባቸው አካባቢዎች ያስገኘውን ውጤት በማገናዘብ፤ ከዚያ በሚቀመሰው ልምድ በመነሳት ከሃገራችን ሁኔታ ጋር በሚጣጣም መልክ በስራ ለመተርጎም የሚቻልበትን እቅድ ከወዲሁ ለመተለም የሚያስችለውን ዘዴና ብልሀት ከወዲሁ አጢኖና ተዘጋጅቶ ለመጠበቅ፤ ዛሬ ስርዓቱን ለማስወገድ ሰላማዊም ሆነ የትጥቅ ትግል የሚያካሂዱ የፖለቲካ ድርጅቶች፤ የህዝባዊ ድርጅቶች፤ በተለይም በመስኩ ዕውቀት ያላቸው አዋቂዎች/ምሁራን ጉዳዩን ጉዳያቸው በማድረግ የተለየ ትኩረት በመስጠት በሴሚናርና፤ በሌላም ተመሳሳይ መንገዶች ሁሉ ትምሕርት በመስጠት የሕዝብን ንቃተ ህሊና ለማጎልበት በሚረዳ መልክ እንዲካሄድ ለማድረግ እስከሆነ ድረስ ጥያቄው ተነስቶ መስተናገዱ የሚደገፍና የሚነቃቃም ነው። በምንም ምክንያት ተቃውሞ አይኖርም።

ከዚህ ባለፈ ግን፤ ዛሬ የሃገራዊ እርቅ ደርግ አቋቁመን፤ እርቅ መደረግ አለበት የሚባለው ልፈፋ „ከብት ባልዋለበት ኩበት ለቀማ“ ወይም „ጋሪው ከፈረሱ ቀደመ“ እንደሚባለው ነው የሚሆነው። ከዚያም አልፎ የትግሉን አቅጣጫ ማሳት ነው የሚሆነው። ከትግሬ ሕዝብ ነጻነት ግንባር ጋር እርቅ እናድርግ የሚባል ከሆነ፤ ይህ የፖለቲካ ድርጅቶች አቲሆ ባቲሆ ካልሆነ በስተቀር ከሃገራዊ እርቅ ጋር ዝምድና የሚኖረው አይደለም። ዘረኛ ስርዓት ከመወገድ ባነሰ የሚሰጠው ዕድል አይኖረውም። የስርዓቱ አራማጆችም የሚሉት እኛ ካቃተን ጥለን መሄድ ነው እንጂ፤ የኛ ፐሮግራም ስራ ላይ ከማይውልበት ውልም ሆነ ስምምነት የምንደርስበት ምክንያት አይኖርም ነው። ለነገሩማ ከትግራይ ሕዝብ ነጻነት ግንባር (TPLF) ጋር ልደራደር የሚል ሃይል ቢኖር፤ ድርድር የሰጥቶ መቀበል ጉዳይ ነውና እንግዲህ ለTPLF ከዘረኝነቱ ጥቂትም ቢሆን ሊተውለት ይገበል ማለት ነው። ይህን ማድረግ ይቻላል? ያለበለዚያ የTPLF ስርዓት የህልውናው መሰረት የሆነችው ዘረኝነት ከተናደች እንደጭስ በንኖ እንደሚጠፋ እሱም እኛም በወግ እናውቀዋለን። ገለሰቦችም ሆንን፤ ድርጅቶች ተቃዋሚዎች እራሳችን የተናገርነውን እራሳችን መልሰን ከማዳመጥ ቆጠብ ብለን TPLF የሚለውን ልብ ብለን እናዳምጥ፤ TPLF በውድም ሆነ በግድ መደራደር የሚባለውን ነገር ይሞከረዋል ብላችሁ አታስቡ። እኔ አንድ ጊዜም እንኳን በምርጫ ብሸነፍ አገሪቱ ትበታተናለች ሲለን፤ እንዲገባን የሚያስፈልገው አንድ ነገር ብቻ ነው። ገፍቶ ሲመጣብኝ አጥፍቼ እጠፋለሁ ማለት ነው ። በፈለጋችሁት አቅጣጫ አገላብጣችሁ ተርጉሙት ሌላ ጠብ ሊል የሚችል ትርጉም አይገኝም። በዚህ አልስማማም የሚል ካለ፤ አንተ ካልገዛኸን መበታተናችንን እንዴት አወቅኸው ብሎ ጠይቆ መልሱን ያደርሰን ዘንድ አደራ እላለሁ። በዚህም የሚከተለውን ማስታወሻ አስመዝግቤ ልሰናበት፤

ሀ. ባሁኑ ጊዜ በዚያም ሆነ በዚህ፤ ከኢትዮጵያ ጋር በተያያዘ የሃገራዊ ዕርቅን ጉዳይ በሚያነሱ ብዙ ወገኖች እንደምሳሌ ተደርጎ በተደጋጋሚ የሚጠቀሰው የደቡብ አፍሪካው የዕውነትና የእርቅ ደርግ „Truth and Reconciliation Commission“ የሚባለው ነው። ምሳሌው ለኢትዮጵያም ግብአት ይኖረዋል ከተባለ ክፋት አይኖረውም። መታወቅ ያለበት ግን፤ ይህ ደርግ የተቋቋመው የአፓርታይድ ስራዓት ተወግዶ የሃገራዊ አንድነት መንግሥት ተመስርቶ በዚህ ሃገራዊ አንድነት መንግሥት በራሱ አነሳሽነት ጭምር የተቋቋመ ደርግ መሆኑን ነው።

ለ. ሌላው በምርጫ ዘጠና-ሰባት ወቅት የኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ ሃይሎች ሕብረት (ኢዴሃሕ) ለሕዝብ አቅርቦት በነበረው አማራጭ ሰነድ „…የኢሕአዴግ መሪዎች በሕዝብ ትግል ከጥፋት ሂደታቸውና ይዞታቸው እንዲገቱ ከተደረገ በሁዋላ፤ አንድ የዴሞክራሲያዊ ሽግግር አገር-አቀፍ ጉባዔ“ ያስፈልጋል ካለ በሁዋላ የጉባዔው ተካፋይ ስለሚሆኑት የህብረተሰብ ክፍሎችንም በዝርዝር አስቀምጦ፤ „አገራችን ወደ ዴሞክራሲያዊና ሕገ-መንግሥታዊ ሥርዓት እናሸጋግር ካልን የዚህ ሃላፊነት በዚሁ ጉባዔ ለሚመረጥ „የዴሞክራሲያዊ ሂደት (ዴሞክራታይዜሽን) ኮሚሺን“ ይተውና „ትርጉም ያለው ብሔራዊ ዕርቅ ወርዶ የተረጋጋ ሕብረተሰብ እውን ለማድረግ ደግሞ በዚሁ ጉባዔ የሚሰየም የብሔራዊ ዕርቅ ኮሚሺን እንደሚያስፈልግ ….“ በማለት ያስቀመጠውን ስንመለከት፤
ቀደም ሲል በቁጥር „1 የተመረጠ መንግሥት ቢቋቋምም እንኳን ….“ በሚል ካስቀመጥኩት ጋር ስለሚጣጣም􏰀 ሀሳቤ ቢያንስ በምሳሌዎቹ ዙሪያ የቆሙትን ወገኖች አወንታዊ ምላሽ እንደማያጣ እምነት አለኝ።
ሰላማዊ ጊዜ ይታዘዝልን
ashebir@t-online.de


The post ሀገራዊ (ብሔራዊ) ዕርቅ በኢትዮጵያ appeared first on Zehabesha Amharic.

ቦንጋ አካባቢ የሚገኝ የተፈጥሮ ጫካ ተቃዋሚ ድርጅቶች እየተንቀሳቀሱበት ነው በሚል ምክንያት በገዢው መንግስት እንዲቃጠል ተደረገ

$
0
0

የኢህአዴግ ባለስልጣኖች ቦንጋ አካባቢ የነበረ የተፈጥሮ ጫካ ተቃዋሚ ድርጅቶች እየተንቀሳቀሱበት ነው በሚል ምክንያት እንዲቃጠል ማድረጋቸውን የትህዴን ድምጽ ዘገበ::
Zehabesha News
የትህዴን ምንጭ የዜና ምንጮቹን ጠቅሶ እንደዘገበው በደቡብ ክልል ቦንጋ አካባቢ የሚገኝ ሰፊ የተፈጥሮ ጫካ በአካባቢው ህዝብ ለዘመናት ጠብቆት የኖረ ሃብት ሲሆን የገዢውን ስርአት በመቃወም እየታገሉ ያሉት ተቃዋሚዎች የሚንቀሳቀሱበት አካባቢ ነው ብለው ስጋት ላይ የወደቁት የስርአቱ ካድሬዎች እሳት ለኩሰው እንዲቃጠል ማድረጋቸውና ይህን እኩይ ተግባር የታዘበው የአካካባቢው ህዝብም በስርአቱ ላይ ጠንካራ ተቃውሞ እንዳስነሳ ለማወቅ ተችሏል።

የአካባቢው ህዝብ እየተቃዎመ በነበረበት ሰዓት እንደገለፀው በአፋችሁ ልማት አልሙ፤ ድህነት አጥፉ እያላችሁ በተግባር ግን መተኪያ የሌላቸውን የተፈጥሮ ሃብቶችን እያቃጠላችሁ ነው በማለት ሃይለኛ ተቃውሞ ማንሳታቸውን መረጃው ጨምሮ አስረድቷል።

The post ቦንጋ አካባቢ የሚገኝ የተፈጥሮ ጫካ ተቃዋሚ ድርጅቶች እየተንቀሳቀሱበት ነው በሚል ምክንያት በገዢው መንግስት እንዲቃጠል ተደረገ appeared first on Zehabesha Amharic.


(የሳዑዲ ጉዳይ) ስራቸውን እየሰሩ ነው፣ እኛ ተዘናግተናል ! * በሳውዲ እስር ቤት የኢትዮጵያውያን መልዕክት

Next: Hiber Radio: የኦጋዴን ነጻ አውጭ ስድስት የአገዛዙን ልዩ ሀይል አባላት መማረኩ፣ጠፍቷል የተባለው የአሜሪካ አየር ሀይል ባልደረባ የሆነው ትውልደ ኢትዮጵያዊ ከአገር ቤት ሲመጣ እጁን ለፖሊስ ሰጠ፣ ዶ/ር መረራ ትግላችንን እንቀጥላለን አሉ፣ ሳውዲ አረቢያ የሐጂ ተጓዦችን አዲስ የመቆጣጠሪያ ብራስሌት እንዲያደርጉ ልታስገድድ ነው፣ አቶ ማሙሸት መስቀል አደባባይ አመጽ አስነስተዋል በተባሉበት ዕለት ፍ/ቤት እንደነበሩ አስመሰከሩ፣የምርጫ ታዛቢዎች ላይ የተጀመረው እስር ቀጥሏል፣ የሼህ ካሊድ፣የብጹዕ አቡነ መቃሪዮስ እና የአክቲቪስት ታማኝ በየነ ንግግር እና ሌሎችም
$
0
0

ነቢዩ ሲራክ

በሳውዲ ጅዳ ሪያድና በተለያዩ ከተሞች ህገ ወጥ የተባሉትን የውጭ ዜጎች የማጥራቱ ዘመቻ ደመቅ ብሎ ባይሰማም በሂደት ላይ ነው ። በያዝነው ሳምንት ጅዳ ውስጥ በርካታ ኢትዮጵያውያን በሚኖሩባቸው በተለያዩ የከተማዋ ክፍሎች በተደረገ ፍተሻ ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ህጋዊ መኖርያ ፍቃድ ያላቸው እህቶችና ወንድሞች ቤት ለቤት በሚደረገው አሰሳ ተይዘዋል ።
nebyu sirak
በአሰሳ ፍተሻው ተይዘው በወህኒ የሚገኙት እንዳደረ ሱኝ መረጃ ከሆነ አያያዛቸው መኖርያ ፈቃድ ከሌላቸው ጋር በመገኘታቸውን ጨምሮ በአንድ ህንጻ ውስጥ ህገወጦች ተገኙ ተብሎና ሌላም ሌላ ምክንያቶች የተሰጣቸውን መሆኑን መረጃ አድርሰውኛል። በተለይም ህጋዎ መኖርያ ፍቃድ እያላቸው ከነ ልጅ ቤተሰቦቻቸው የተያዙት ወገኖች ቢቻል የመንግስት ተወካዮች ጉዳዩን ከአሰሪዎቻቸውና ከሳውዲ መንግስት ሃላፊዎች ጋር ተነጋግረው በዋስ እንዲዎጡ እንዲረዷቸው ተማጽነዋል !

እኒህ ወገኖች እያለቀሱ ባስተላለፉት መልዕክት እንዲህ የሚል ይገኝበታል …” … የረባ ልብስ ሳንለብስ ቤተ ተሰብሮ ተይዘን ፣ በባዷችን ወደ ሀገር ግቡ እየተባልን ነው ! ለአመ ታት የሰበሰብነውን ቁሳቁስ ፣ ሀብት ንብረት ሳንሰበስብ ቤተሰቦቻችን በትነን ወደ ሀገር መሸኘት የለብንም ፣ የኢትዮ ጵያ መንግስት ተወካዮች ከአሰሪዎቻችንና ከመንግስት ጋር ተነጋግረው ያስፈቱን ፣ ማስፈታት ካልቻሉ ንብረታችን ሰብስበን የምንሄድበት መንገድ መንግስታችን ያመቻችልን ዘንድ ድምጻችን አሰማልን !” ብለውኛል ! መልዕክቱ ለሚመለከታችሁ ሁሉ ይድረስ !
እነሱ ስራቸውን እየሰሩ ነው ፣ አቁሙ አይባሉም ፣ እነማን እንደሆኑ እያወቅን ፍን ደጋግመን ተዘናጋን ! … ደጋግመን አበሳን ለመክፈል ተገደድን ፣ እንጠንቀቅ ፣ ከመጭው አደጋ ለመዳን !
ቸር ያሰማን !
ነቢዩ ሲራክ
ግንቦት 23 ቀን 2007 ዓም

The post (የሳዑዲ ጉዳይ) ስራቸውን እየሰሩ ነው፣ እኛ ተዘናግተናል ! * በሳውዲ እስር ቤት የኢትዮጵያውያን መልዕክት appeared first on Zehabesha Amharic.

Hiber Radio: የኦጋዴን ነጻ አውጭ ስድስት የአገዛዙን ልዩ ሀይል አባላት መማረኩ፣ጠፍቷል የተባለው የአሜሪካ አየር ሀይል ባልደረባ የሆነው ትውልደ ኢትዮጵያዊ ከአገር ቤት ሲመጣ እጁን ለፖሊስ ሰጠ፣ ዶ/ር መረራ ትግላችንን እንቀጥላለን አሉ፣ ሳውዲ አረቢያ የሐጂ ተጓዦችን አዲስ የመቆጣጠሪያ ብራስሌት እንዲያደርጉ ልታስገድድ ነው፣ አቶ ማሙሸት መስቀል አደባባይ አመጽ አስነስተዋል በተባሉበት ዕለት ፍ/ቤት እንደነበሩ አስመሰከሩ፣የምርጫ ታዛቢዎች ላይ የተጀመረው እስር ቀጥሏል፣ የሼህ ካሊድ፣የብጹዕ አቡነ መቃሪዮስ እና የአክቲቪስት ታማኝ በየነ ንግግር እና ሌሎችም

$
0
0

ጋዜጠኛ ሃብታሙ አሰፋ

ጋዜጠኛ ሃብታሙ አሰፋ


የህብር ሬዲዮ የግንቦት 23 ቀን 2007 ፕሮግራም

ዶ/ር መረራ ጉዲና የመድረክ ም/ሊቀመንበርና የኦፌዲን ሊቀመንበር ተቃዋሚዎች ከተዘረፈው ምርጫ ማግስት ስለሚኖራቸው ሚና ከህብር ሬዲዮ ጋር ያደረጉት ውይይት (ሙሉውን ያዳምጡ)

አክቲቪስት ታማኝ በየነ በቬጋስ ካደረገው ንግግር የተወሰደ( ያዳምጡት)

ሼህ ካሊድ የፈርሰት ሒጅራ ኢማም በቬጋስ ለኢሳት ገቢ ማሰባሰቢያ ላይ ተገኝተው ከተናገሩት

ብጹዕ አቡነ መቃሪዮስ በቬጋስ ተገኝተው ከተናገሩት (ሙሉውን ያዳምጡት)

የፊፋ ባለስልጣናት የሙስና ቅሌት ፣ የአሜሪካና የአውሮፓ በፊፋ ጉዳይ ጣልጋ ማስገባት ለምን ፈለጉ ?(ልዩ ጥንቅር)

ሌሎችም

ዜናዎቻችን

ትውደ ኢትዮጵያዊው የአሜሪካ አየር ሀይል ባልደረባ ጠፍቶ ሲመጣ ለጸጥታ ሰዎች እጁን ሰጠ

ዶ/ር መራራ ጉዲና ትግላችን ይቀጥላል አሉ

ተቃዋሚዎች የዛሬ 30 እና 40 ዓመት አጀንዳቸውን ወደ ጎን አድርገው ተባብረው መታገል አለባቸው ብለዋል

የአፍሪካ ህብረት ታዛቢዎችን አጣጣሉ

የሕዝብ ድምፅ ይከበር ያሉ ከ6 መቶ በላይ የመድረክ ጠንካራ አባሎችና ታዛቢዎች ታስረዋል

በኢትዮ ሶማሊያ ድንበር ኦብነግ 6 ታጣቂዎችን ማረኩ አለ

አቶ ማሙሸት መስቀል አደባባይ ሕዝብ አሳመጹ በተባለው እለት ምርጫ ቦርድን ከሰው ፍ/ቤት እንደነበሩ አስመሰከሩ

የሳውዲ መንግስት ኢትዮጵያውያንን ጨምሮ ለሐጂ ወደ አገሪቱ የሚገቡ አዲስ የኤሌክትሮኒክስ ብራስሌት እንዲያጠልቁ ለማስገደድ በዝግጅት ላይ መሆኑ ተነገረ

ሁበር በቬጋስ ከወር በኋላ ሥራ እጀምራለሁ አለ

በኢትዮ ሶማሊያ ድንበር አገዛዙ ሠራዊትና በአካባቢው ተወላጆች መካከል በተፈጠረው ግጭት በርካቶች ጉዳት ደረሰባቸው

የአገዛዙ ወታደሮች ጉዳት የደረሰባቸውን ወጣቶች ህክምና እንዲያገኙ ከለከሉ

የሚሉና ሌሎችም ዜናዎች አሉን

The post Hiber Radio: የኦጋዴን ነጻ አውጭ ስድስት የአገዛዙን ልዩ ሀይል አባላት መማረኩ፣ጠፍቷል የተባለው የአሜሪካ አየር ሀይል ባልደረባ የሆነው ትውልደ ኢትዮጵያዊ ከአገር ቤት ሲመጣ እጁን ለፖሊስ ሰጠ፣ ዶ/ር መረራ ትግላችንን እንቀጥላለን አሉ፣ ሳውዲ አረቢያ የሐጂ ተጓዦችን አዲስ የመቆጣጠሪያ ብራስሌት እንዲያደርጉ ልታስገድድ ነው፣ አቶ ማሙሸት መስቀል አደባባይ አመጽ አስነስተዋል በተባሉበት ዕለት ፍ/ቤት እንደነበሩ አስመሰከሩ፣የምርጫ ታዛቢዎች ላይ የተጀመረው እስር ቀጥሏል፣ የሼህ ካሊድ፣የብጹዕ አቡነ መቃሪዮስ እና የአክቲቪስት ታማኝ በየነ ንግግር እና ሌሎችም appeared first on Zehabesha Amharic.

፬ኛው የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ጠቅላላ ጉባኤ የጋራ አቋም መግለጫ

Previous: Hiber Radio: የኦጋዴን ነጻ አውጭ ስድስት የአገዛዙን ልዩ ሀይል አባላት መማረኩ፣ጠፍቷል የተባለው የአሜሪካ አየር ሀይል ባልደረባ የሆነው ትውልደ ኢትዮጵያዊ ከአገር ቤት ሲመጣ እጁን ለፖሊስ ሰጠ፣ ዶ/ር መረራ ትግላችንን እንቀጥላለን አሉ፣ ሳውዲ አረቢያ የሐጂ ተጓዦችን አዲስ የመቆጣጠሪያ ብራስሌት እንዲያደርጉ ልታስገድድ ነው፣ አቶ ማሙሸት መስቀል አደባባይ አመጽ አስነስተዋል በተባሉበት ዕለት ፍ/ቤት እንደነበሩ አስመሰከሩ፣የምርጫ ታዛቢዎች ላይ የተጀመረው እስር ቀጥሏል፣ የሼህ ካሊድ፣የብጹዕ አቡነ መቃሪዮስ እና የአክቲቪስት ታማኝ በየነ ንግግር እና ሌሎችም
$
0
0

eotc-ssd-4th-gen-assembly-participantsበሐዋርያዊት፣ ጥንታዊት እና ብሔራዊት ቤተ ክርስቲያናችን ህልውና እና ዕድገት ፊት ከተጋረጡትና አፋጣኝ እልባት ከሚሹት የዘመናችን የውስጥ ችግሮች እና የውጭ ተግዳሮቶች ውስጥ ሙስና እና ኑፋቄ ቀዳሚዎቹ ናቸው፡፡ አንዱ የሌላው መተላለፊያ፣ መንሥኤ እና ውጤት እየኾኑ ለቤተ ክርስቲያን ተቋማዊ ለውጥ የተደረጉ ጥረቶችን ሲያመክኑ፤ የመዋቅር እና የአደረጃጀት አቅሟን ሲያዳክሙ ቆይተዋል፡፡

በአዲስ አበባ ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የሚያዝያ ፳፯ ቀን ፳፻፯ ዓ.ም. መግለጫ እንደተመለከተው፣ በቅዱስ ሲኖዶስ ተወግዘው ከተለዩ በኋላ በቅጥር ወደ አስተዳደራዊ እና የአገልግሎት መዋቅሯ የገቡ የፕሮቴስታንታዊ ተሐድሶ መናፍቃን መኖራቸው ሙስና እና ኑፋቄ የተሳሰሩ እና የሚመጋገቡ ለመኾናቸው ግልጽ አስረጅ ነው፡፡

ከግንቦት ፳፩ – ፳፫ ቀን ፳፻፯ ዓ.ም. በጠቅላይ ቤተ ክህነት የመሰብሰቢያ አዳራሽ ሲካሔድ ቆይቶ ለጽርሐ መንበረ ፓትርያርኩ አርዕድ አንቀጥቅጥ በኾኑ፤ መልካም አስተዳደር እና ፍትሐዊ ፍርድ በሚጠይቁ መዝሙሮች ትላንት ማምሻውን የተጠናቀቀው ፬ኛው ዓመታዊ ሀገር አቀፍ የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ጠቅላላ ጉባኤ፣ በጋራ አቋም መግለጫዎቹ በቀጥታ ይኹን በአማራጭ ያረጋገጠውም ይህንኑ እውነታ ነው፡፡

* * *


ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት

ብፁዕ አቡነ ሉቃስ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ እና የሰቲት ሑመራ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ
ብፁዕ አቡነ ማቴዎስ የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ እና የወላይታ ኮንታ እና ዳውሮ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ
ብፁዕ አቡነ ቀሌምንጦስ የሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ የበላይ ሓላፊ ሊቀ ጳጳስ፣ በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የፓትርያርኩ እንደራሴ ሊቀ ጳጳስ፣ የጉራጌ ስልጤ ከምባታ እና ሐዲያ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ
ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት
የጠቅላይ ቤተ ክህነት የመምሪያ ሓላፊዎች
ከተለያዩ አካላት ጥሪ የተደረገላችኹ የክብር እንግዶች፤

እኛ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ጠቅላላ ጉባኤያትን ወክለን በ፬ኛው የሀገር አቀፍ የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት አጠቃላይ ጉባኤ ላይ የተሳተፍን የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ጠቅላላ ጉባኤ አባላት ከግንቦት ፳፩ – ፳፫ ቀን ፳፻፯ ዓ.ም. ላለፉት ሦስት ቀናት÷ የማደራጃ መምሪያው ዓመታዊ የአገልግሎት ዘገባ፤ ከ37 አህጉረ ስብከት የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት እና የሰንበት ት/ቤቶች ዋና ክፍሎች ሪፖርቶች፤ የሰንበት ት/ቤቶች አባላት በኾኑ ባለሞያዎች በቀረቡ ጥናታዊ ጽሑፎች ላይ ሰፊ ውይይት አድርገናል፡፡

በመምሪያው ዘገባም ኾነ ከ37 አህጉረ ስብከት የመጡ ተወካዮች ያቀረቡት ሪፖርት ሰንበት ት/ቤቶች እጅግ በርካታ ተግባራት እያከናወኑና የቤተ ክርስቲያንን ተልእኮ ለማፋጠን እየተጉ መኾኑን አስገንዝቧል፡፡ ኾኖም ግን በየአህጉረ ስብከቱ የሚታዩ፡-

  • የመናፍቃን እና የአፅራረ ቤተ ክርስቲያን ተጽዕኖ፤
  • በየአጥቢያ ቤተ ክርስቲያን እየደረሱ ያሉ የአስተዳደር በደሎች፤
  • የበጀት እና የመምህራን እጥረት፣ የአዳራሽ እጥረት፤
  • የአንዳንድ አህጉረ ስብከት ስፋት ለትራንስፖርት አመቺ አለመኾን፤

አገልግሎቱን እየተገዳደሩ ያሉ ዋና ዋና ችግሮች ኾነው ተዘግበዋል፡፡

‹‹የሰው ኃይል አያያዝ በሰንበት ት/ቤት›› በሚለው ጥናታዊ ጽሑፍ መነሻነት በተደረገው ውይይትም ለቤተ ክርስቲያን ኹለንተናዊ ዕድገት ወሳኝ የኾነው የሰው ኃይል መኾኑን በማመን የቤተ ክርስቲያን አካላት በሙሉ በተለይም ሰንበት ት/ቤቶች ትኩረት ሰጥተን ልንሠራበት እንደሚገባ ተገንዝበናል፡፡ በማያያዝም ‹‹የኢኮኖሚ ግንባታ ለቤተ ክርስቲያን›› በሚለውም ጥናት፣ የኢኮኖሚ አቅም ማነስ÷ የመጠቀምን፣ የመደመጥን፣ የመወሰንን፣ የመተግበርን አቅም ያሳጣል፤ በሌላ በኩል እምነትን ይፈትናል፤ ሥጋዊውን ጥቅም ለማሳካት ሲባል ከቤተ ክርስቲያን መለየትን ያመጣል፤ ብዙ ተባዙ ምድርንም ምሏት ያለውን የእግዚአብሔር ቃል ያስጥሳል፤ ወጣቱንም ለስደት እና ለመከራ እየዳረገ ይገኛል፤ የቤተ ክርስቲያን ተልእኮም እንዳይፋጠን ያደርጋል፡፡

ስለዚኽ ቤተ ክርስቲያን ያላትን ሀብት በአግባቡ በመጠቀም ኢኮኖሚያዊ አቅሟን ልታጠናክር፤ ተሰሚነቷን ልታስከበር ይገባታል፤ ሰንበት ት/ቤቶችም የኢኮኖሚ አቅማቸውን ለማጠናከር የሚያስችሉ ተግባራት ሊሠሩ፤ የቤተ ክርስቲያን መምሪያዎችም ሊያግዟቸው እንደሚገባ ውይይቱ ትኩረት ሰጥቶበታል፡፡

በመጨረሻም በሪፖርቱም ኾነ በጥናታዊ ጽሑፎች የተጠቀሱትን ዋና ዋና ችግሮች በመለየት በተደረገ የቡድን ውይይት ሰንበት ት/ቤት በቀጣይነት በጋራ የምንሠራቸውን እና የምንስማማባቸውን የአቋም መግለጫዎች አውጥተናል፡፡

  1. የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ከ2006 – 2010 ዓ.ም. የታቀደውን የአምስት ዓመት መሪ ዕቅድ በቀሩት ጊዜያት ለመፈጸም እና ለማስፈጸም ቃል እንገባለን፤
  2. የሰንበት ት/ቤቶች አጠቃላይ መሪ ዕቅድ የኹሉም የአጥቢያ ሰበካ መንፈሳውን ጉባኤያት ዕቅድ አካል እንዲኾን እና የጠቅላይ ቤተ ክህነት መምሪያዎችም ኹሉ መሪ ዕቅዱን ከዕቅዳቸው ጋራ በማገናዘብ እንዲያካትቱ ይደረግ ዘንድ እንጠይቃለን፤
  3. መልክአ ምድርን መሠረት ያደረገ የሰንበት ት/ቤቶች ትስስር በማጠናከር ሰንበት ት/ቤቶች ባልተቋቋሙባቸው አጥቢያዎች እንዲቋቋሙ፣ በተቋቋሙባቸው ደግሞ የተጠናከረ አገልግሎት እንዲሰጥባቸው ለማድረግ እንሠራለን፤
  4. የፕሮቴስታንታዊ ተሐድሶ ኑፋቄ ችግሮችን ለማጋለጥ ያስችል ዘንድ ከሀገር አቀፍ የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ጀምሮ እስከ አጥቢያ ቤተ ክርስቲያን ሰንበት ት/ቤት የሚደርስ መረጃ የማሰባሰብ ሥርዐት በመዘርጋት የመረጃ ማሰባሰቡን አጠናክረን እንሠራለን፤
  5. በአኹኑ ሰዓት በቤተ ክርስቲያን ተልእኮ አፈጻጸም ላይ ተጽዕኖ እየፈጠረ ያለው የፕሮቴስታንታዊ ተሐድሶ መናፍቃንን እንቅሰቃሴ ለማስቆም ከቅዱስ ሲኖዶስ ጀምሮ በየደረጃው ያሉ የቤተ ክርስቲያን አካላት አፋጣኝ ርምጃ እንዲወስዱ እንጠይቃለን፤
  6. ቀደም ሲል በአዲስ አበባ ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ስለ ፕሮቴስታንታዊ ተሐድሶ መናፍቃን የቀረበው ማስረጃ ውሳኔ እንዲሰጠው፤ ውሳኔውም ተግባራዊ ይኾን ዘንድ ከቅዱስ ሲኖዶስ ጀምሮ ያሉ የቤተ ክርስቲያን አካላት አስፈላጊውን ርምጃ እንዲወስዱ እንጠይቃለን፤
  7. በአኹኑ ጊዜ አንዳንድ የቤተ ክርስቲያን ሓላፊዎች በሰንበት ት/ቤት ወጣቶች እና አባላት ላይ በተሳሳተ አመክንዮ እያደረሱት ያለው እስር፣ እንግልት እና ወከባ እንዲቆምልን በአጽንዖት እንጠይቃለን፤
  8. ከዚኽ ጋር ተያይዞ የመንግሥት የፍትሕ አካላትም ከአጥፊዎች ጋር በመተባበር የሰንበት ት/ቤት አባላትን ከማሰር እና ከማንገላታት እንዲታቀቡ ይደረግ ዘንድ እንጠይቃለን፤
  9. በቃለ ዐዋዲው እና በ1986 ዓ.ም. ሕገ ደንቡ ላይ የተጠቀሰው የሰንበት ት/ቤቶች የዕድሜ ገደብ እንዲነሣልን በድጋሜ እንጠይቃለን፤
  10. ከሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ አንሥቶ እስከ አጥቢያ ሰንበት ት/ቤቶች የሚደርስ የፋይናንስ ትስስር እና አያያዝ ሥርዐት በመምሪያው በኩል ተጠንቶ እንዲጸድቅልን እንጠይቃለን፤
  11. የቤተ ክርስቲያንን ሀብት እና ንብረት ለግል ጥቅማቸው በማዋል የቤተ ክርስቲያንን አቅም የሚያዳክሙ አማሳኞች ማስረጃ ተጠናቅሮ በአገሪቱ ሕግ መሠረት እንዲጠየቁልን እንጠይቃለን፤
  12. የቤተ ክርስቲያን የፋይናንስ አሠራር ማእከላዊ እንዲኾን እና በባለሞያዎች የሚታገዝ የክትትል እና የቁጥጥር ሥርዐት እንዲኖረው እንጠይቃለን፤
  13. በዘመናችን ሚዲያ በወጣቱ እና በሕፃናት አስተዳደግ ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ እየፈጠረ ስለሚገኝ የቤተ ክርስቲያንን አስተምህሮ በስፋት ለምእመናን ለማዳረስ እንዲቻል በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሚመራ እና የሚተዳደር፤ ቤተ ክርስቲያኒቷንም የሚወክል የቴሌቪዥን መርሐ ግብር እንዲጀመር በአጽንዖት እንጠይቃለን፤
  14. በአኹኑ ሰዓት በቤተ ክርስቲያን ስም ቤተ ክርስቲያንን የማይወክል ትምህርት እና መልእክት የሚያስተላልፉ የቴሌቪዥን መርሐ ግብሮች በተቻለ ፍጥነት እንዲዘጉ አልያም በቤተ ክርስቲያን ስም ከመጠራት እና ከመጠቀም እንዲከለከሉ እንጠይቃለን፤
  15. ለጠቅላላ ጉባኤው ተወካዮቻቸውን ያልላኩ አህጉረ ስብከት ተለይተው በጠቅላይ ቤተ ክህነቱ የማያዳግም ርምጃ እንዲወሰድባቸው እንጠይቃለን፤
  16. በቤተ ክርስቲያናችን መንፈሳዊ እና ልማታዊ ጉዳዮች ከአባቶቻችን ጋር በመኾን ያለንን አቅም አሟጠን በመጠቀም ለቤተ ክርስቲያን ዕድገት እና ልዕልና የበኩላችንን ድርሻ እንወጣለን፤
  17. የቤተ ክርስቲያናችንን ኹለንተናዊ ችግር ለመፍታት ከመንፈሳዊ ኰሌጅ ምሩቃን(ቴዎሎጅያን) ጋር ተባብረን የምንሠራ መኾናችንን እንገልጻለን፤
  18. የአዲስ አበባ ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ያቀረበው ጥያቄ የኹላችንም አቋም ስለኾነ አፋጣኝ መልስ እንዲሰጠው እንጠይቃለን፡፡

ግንቦት ፳፫ ቀን ፳፻፯ ዓ.ም.

Source:: haratewahido

The post ፬ኛው የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ጠቅላላ ጉባኤ የጋራ አቋም መግለጫ appeared first on Zehabesha Amharic.

ፈጣን ሩጫ አይሉት ማራቶን የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ –የተርጓሚው ማስታወሻ

$
0
0

ከቢላል አበጋዝ፡ ዋሽግቶን ዲ፡ሲ

ይህ ጽሁፍ ዘኢኮኖሚስት ከሚያወጣቸው ኁሉ ብናየውና ብንወያይበት ይጠቅማል በሚል አሳብ ተተርጉሞ ቀርቧል።እራሱን ሳንሱር እያደረገ እንደጻፈው ማየት አያስቸግርም። ከዚህ ትርጉም እንደምታዩት ምዕራብ፡ ምስራቁ ህወሀት መሩ መንግስት ተብዬ ላይ ሁሉም ተስፋ መቁረጡን በግልጥ ያሳያል። የቻይና አምባሳዶር  እቅጩን ይናገራል።ያፈርጠዋል። እዲያው አበዛችሁት ዓይነት ነው።በቻይና የምጣኔ ሃብት ግንባታው ሊሰራ የቻለው የቻይና ኮሚኒስት ፓርቲ የህዝቡን ድጋፍ  ይዞ ነው።ዛሬ ወያኔ ከህዝብ ተገልሎ ፈርቶ አደር  ሆኖ እያነከሰ ነው።ህወሀቶች ቻይና መልሳ ካፒታሊዝምን ተማሩ የምትላቸው ከጊዜው ጋር መራመድ የማይችሉ፤መለስ ከሞተ ወዲያ እንኳን የሰራውን ጥፋት ማየት ያልቻሉ ትቷቸው እንደሄደ ተገትረው የቀሩ ጉዶች ናቸው።ዘኢኮኖሚስት ከመለስ ሞት በኋላ በሰላም በመንግስትነት ተሸጋገሩ ይላል ሌላ ሊሆን እንደሚችል ሁሉ።ዛሬ እየሆነ ያለውን፤የምርጫውን ቧልት፤በሰሜን ኢትዮጵያ ወያኔን ስለሚያጫንቀው ሁኔታ አይተነፍስም።ወያኔ ላይ ያንጃበበው ዳመናም አይታየውም ወይም አይቶት አይናገርም።ለኛ ገሀድ የሆነውን።

የውጭ ተንታኝ ይሳሳታል።እኛ ወያኔ ይወድቃል ህዝብ ተመሯል አይሰነብትም ስንል።በኢትዮጵያ ወያኔን ቀጣይ አድርጎ ያያል። ወያኔዎች ዙሪያው ገደል ሆኖባቸው፤እርስ በርስ እየተወነጃጀሉ ለመሆናቸው ምልክቶች እየታዩ ነው። ወያኔ ዳሩ እየላላበት ነው። መሃሉም ረመጥ እሳት ይሆንበታል። በመጣበት ዘዴ ሊሸኝ። ትርጉሙ እነሆ።

ከቢላል አበጋዝ፡ ዋሽግቶን ዲ፡ሲ

 

ፈጣን ሩጫ አይሉት ማራቶን_ የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ

ይህ ጽሁፍ ዘ ኢኮኖሚስት May 30th 2015 ያወጣው ጽሁፍ ትርጉም ነው።

ከመላው አፍሪካ በሙሉ እንደ ኢትዮጵያ አድርጎ ቻይና እንደ መራሄ ኮከብ፤ዋና ምሳሌ ተደርጋ የምትወሰድበት የለም።ይሄው ኢትዮጵያ በሜይ 24 እዚህ ግባ የማይባል ውጤቱ ቀድሞ የታወቀ፤ምርጫ አካሂዳለች።ያው ለነባሩ ፓርቲ አዲስ አገዛዝ ዘመን የሚለግስ።ከአሃጉሩ በህዝብ ብዛት ሁለተኛ፤በፍጥነት ታዳጊ ኢኮኖሚ ያላት  ኢትዮጵያ ከኮሚኒስት ቻይና ጋር የጠበቀ የአስተሳሰብ ዝምድና አላት።የኢትዮጵያም ባለስልጣናቶችዋን  ወደ ቻይና የፓርቲ ትምርት ቤት ትልካለች።ኢትዮጵያኑ በቻይና ኢንዱስትሪ የማስፋፋትን ወንጌልን፤እንዲዋሀዱና ጠንካራ ማከላዊ የማያላውስ ጨቌኝ መንግስትን ባለብዙ ዘውጎች ያውም ያለመስማማትም ታሪክ ያላቸላቸው ህዝቦችን ስለመግዛት፡ያጠናሉ።

234

ዛሬ ከቻይና ጋር ሁሉም አልጋባልጋ አይደለም። አዲሱ የቻይና አምባሳዶር ያለፈው ፌብሩአሪ አዲስ አበባ ሲደርሱ ለወዳጆቻቸው ያልታሰበ አጉል መልዕክት አድርሰዋል። አምባሳደር ሊ ፋን በዝግ ችሎት የወያኔን ባለስልጣናትን ያለፈው ብቸኝነትን ትታችሁ፤ኢኮኖሚያችሁን ለውድድር ክፈቱት ብለዋል።ንዋይም ዜናም በማዕቀብ መያዙን እያመልከቱ።ባንክና ቴሌ አሰራራቸው የዘመነ ሎጥ ነው።ነጋዴዎች ተመረዋል።ንግድ ወደ ኋላ ቀርቷል።ላመታት ወያኔን ሲያመሰግኑ የኖሩት ቻይኖች ዛሬ ልክ እንደምእራብያውያን ተችዎች ሁሉ ያማርራሉ።

  [ሰንጠረጁ የሚያሳየው የኢትዮጵያን በኢንተርኔትና ቴሌ እጅግ ኋላ መቅረትን ነው።]እአአ 2013 የተቀናበረ ሪፖርት የተወሰደ ከመቶ ሰዎች ምን ያህሉ ግለጋሎት ያገኛሉ በሚል የተጠና።

___________________

የችግሩ መሰረት ድፍረት የለም።በኢትዮጵያ መንግስት ውስጥ ያሉ፤የገዥው ፓርቲ አባላት የጸጥታ ተቋሙን የሚቆጣጠሩትም መሻሻሎችን ማድረግ ብቻ የኢኮኖሚ እድገትና የፖለቲካ መረጋጋትን እንደሚያመጡ ያምናሉ። ሊተገብሩአቸው ግን  ቀርፋፎች ናቸው።

የመንግስቱ ቀዳማይ ፍላጎት ኢንዱስትሪን ማስፋፋት ነው።ነገር ግን ነጋዴዎች በቢሮክራሲ ተተብትበው ከንዋይም ማንቀሳቀስ ታግተዋል።ባለስልጣናት ሁዋጅያንን ያመለክታሉ።ሁዋጅያንን የቻይና በኢትዮጵያ የጫማ ፋብሪካ ነው።በጥቂት አመታት የሰራተኛን  ቁጥርን ከ600 መቶ ወደ 3 ሺ 600 ያደረሰ ነው።ኢትዮጵያ ታዲያ መቶዎች ሁዋጅያንን ትፈልጋለች። ኢንዱስትሪ ሳይስፋፋ 80 % ግብርናን ከማሻሻል በኋላ የሚተርፈውን የሰው ሀይል የምታደርስበት መኖር አለበት።

መንግስት ኢንዱስትሪ መስፋፋትን ለመርዳት መንገጎች ይሰራል፤ባቡር ሃዲዶች ይዘረጋል፤የሀይል ማመንጭያ ጣቢያዎችን፤ግድቦችን ልክ ቻይና እዳረገችው ቅጅውን ይተገብራል።እኒህ ተግባሮች በኦፊሴል የሚታወቀውን የአስር እጅ የኢኮኖሚ ዕድገት አስከትለዋል።ምንም እንኳ ዕድገቱ ሰባትና ስምንት እጅ ነው ተብሎ በውጭ ጠበብት ቢነገርም።የዋጋ ግሽበት ወደ አንድ አሃዝ ወርዷል።ሆኖም ባለፉት ሶስት ዓመታት የዓለም  የንግድ ድርጅቶችን ለመቀላቀል የሚደረግ ጥረት የለም።ስራ የሚያንቀሳቅስ የውጭ ካፒታል መገኘቱ አስተማማኝ አይደለም።

ያለው መንግስት ቁንጮዎች መንግስታችን ይገለበጣል የሚል ስጋት ለውጦችን ከመግፋት ችላ እንዲሉ አድርጓል።በአንድ በኩል ሲያስቡት የመልካም ውጤታቸው ሰለባ የሆኑ ይመስላል።ዲሲፕሊንና አስተዳደራዊ ረቂቅነት ላለው መንግስት ቁንጮዎች መጨቆኛ መሳሪያዎችን በጃቸው እንዲሆኑ አድርጓል።ይህ ደግሞ በአሃጉሪቱ ያሉ መሰል ጨቋኞቸ ሊመኙት ብቻ የሚችሉት ነወ። አሁን ያለው መንግስት ቁንጮዎች ካልዘረጉት የጭቆና መረብ ተለይተው ለመኖር አይታሰባቸውም።

ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ከ1974 እስከ 1991 እአአ ከነበረው የስበስ ጦርነት በኋላ አገሪቱን ያደሳት መሃንዲስ በ2012 እአአ ከሞተ ወዲህ ሁኔታው እየባሰ መጣ እንጄ የተሻለ ነገር አልሆነም።መለስ በባህሪው ብርታት፤የአእምሮ ችሎታውና በጦርነት ጊዜ ባፈራቸው ጥብቅ ወዳጅነቶች መሰረት የመንግስቱን ወደፊት እንዲሄድ ያደርገው ነበር።እርግጥ ነው የንግዱ ክፍልና ህዝባዊ ድርጅቶችን ይጠላ ነበር።ቢያስ ግን ጋሬጣ የሆኑ ጉዳዮችን ያስወግድ ነበር።ከሞቱ በኋላ መንግስቱ በሰላም ሽግግር አድርጓል።ረዳትጠ/ሚኒስትሩ እንደታቀደው ስልጣን ይዟል።

አሁን ያለው አመራር የስብስብ ነው።አዲሱ ረዳትጠ/ሚኒስትር መለስ አይደለም።መለስ አንዱ መታሰቢያው የተከፋፈለውን ድርጅት መከፋፈሉን መደበቅ ነበር። ዛሬ ሚኒስትሮች ውሳኔ ከማድረግ በፊት የነባር አመራርን ፈቃድ ማግኘት አለባቸው።የትግራይ ተወላጆች መለስ ወገናቸው የሆኑት ጦሩን፤ጸጥታውን፤ ቴሌን፤የውጭ ጉዳይን ይቆጣጠራሉ።እነርሱ ጡረታ እስቲወጡ ወይ እስቲሞቱ ቢያንስ ሌላ አስር ዓመት ይፈጅ ይሆናል።

አዲሱ ጠ/ሚኒስቴር ለውጥ የሚሻ፤ምክንያታዊ ሰው ነው።በአንጻሩ ደካማ ነው።በመጭው ሴፕቴምበር በኢህአዴግ ጉባኤ የፓርቲው መሪነት እንደገና ይጸድቅለት ይሆናል።ግን መሰንበቱ የተረጋገጠ አይደለም።መለስ ለምን እንዳጨው የረሱት ጥቂቶ ናቸው።ከተበታተነው ደቡብ የአገሪቱ ክፍል በመሆኑ ዋናዎቹን ቡድኖች የማይቀናቀን በመሆኑ ነው።

በኢትዮጵያ የሚገኘው የቻይና ህብረተ ሰብ ከፍተኛ አባል ተስፋ በመቁረጥ የአገሪቱ[ኢትዮጵያ] ትልቁ ችግር በቻይና ማእከላዊው መንግስት የክልሎች የበላይ ነው።በኢትዮጵያ ግን ሁሉም ነገር ፌዴራል ነው። የንግድ ቀዬዎች የሚገነቡት በጥናት በተመረጡ ቦታዎች ሳይሆን በኮታ ነው።ከዚህም በላይ እንደ ማኦ መርህ “ፓርቲው ጠመንጃውን ይቆጣጠራል” የሚለው ተረስቷል።ጸጥታ ጠባቂዎቹ ህጉን ራሱን ሆነዋል።

በመጨረሻም የኢትዮጵያ ከፍተኛ መሪዎች ችሎታ ቢኖራቸውም እንደቻይና ችሎታ ያላቸው የመካከለኛ ደረጃ አስተዳዳሪዎች የላቸውም።ባጠቃላይ ብዙ ቻይኖች ኢትዮጵያ በብዙ በየቦታው ባሉ ጉልበተኞች  እደተያዘች ያያሉ።

ቻይኖች የማይተነፍሱት  መእራባውያን ግን የሚናገሩት የፖለቲካ ስርዓቱ የሚያደርሰው ጭቆና እንዳዳከመው ነው። ወጣቶች ተቆጥተዋል።ስራ አላገኙም።የብሶት መወጫቸው፤መተንፈሻቸው ቶሎ ተዘግቷል። አስተዋይ የተቃዋሚ መሪዎች ለስደት፡ለእስራት ይዳረላሉ።ይህ ደግሞ ለአክራሪዎች ቦታውን ክፍት ያደርጋል። የዩኒቨርሲቲ ቁጥሮች በርከቷል ግን ለብሩሃኑ ተመራቂዎች የተዘጋጀ ስራ የለም።

ፈርቶ አደርሮች ምክንያት ኢትዮጵያ አጣብቂኝ ውስጥ ትገኛለች።ባላት አስደናቂ እድገት የተነሳ ለጥቂት ጊዜ አንከስ እያለችትሄድ ይሆናል።የሀይል ማመንጫዎችዋም ተጨማሪ ድጋፍ ይሰጥዋት ይሆናል። ኢትዮጵያ ቀርቶባታል መሆን ትችል የነበረውን አስደናቂ  መሆን አልሆነችም።

http://www.economist.com/news/middle-east-and-africa/21652307-africas-most-impressive-economic-managers-suffer-excessive-caution-neither

 

The post ፈጣን ሩጫ አይሉት ማራቶን የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ – የተርጓሚው ማስታወሻ appeared first on Zehabesha Amharic.

በሃመር ወረዳ ከፍተኛ እልቂት መድረሱን የአካባቢው ነዋሪዎች ገለጹ

$
0
0

ግንቦት ፳፩ (ሃያ አንድ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በደቡብ ክልል በደቡብ ኦሞ ዞን በሃመር ወረዳ በዲመካ ከተማ እና አካባቢዋ የሚኖሩ አርብቶአደሮች ” እኛ ድምጽ ሳንሰጥ” እንዴት ኢህአዴግ አሸነፈ ይባላል በሚል ካለፈው ሰኞ ጀምሮ ከጸጥታ ሃይሎች ጋር ሲታኮሱ መቆየታቸውን የሚናገሩት የአካባቢው ነዋሪዎች፣ አንድ ሻለቃ ጦር እና የፌደራል አባላት ወደ አካባቢው በመንቀሳቀስ በወሰዱት እርምጃ ከፍተኛ ጉዳት ደርሷል። አንዳንድ የአካባቢው ነዋሪዎች አደጋ የደረሰባቸውን ሰዎች ቁጥር በመቶዎች ያደርሱታል።
የአካባቢው ሰዎች እንደሚሉት አርብቶ አደሮች 5 የመከላከያ ሰራዊት አባላትን ያቆሰሉ ሲሆን፣ ቁስለኞችም በሄሊኮፕተር ተወስደዋል። በአርብቶ አደሮች በኩል የተገደሉትን ሰዎች በትክክል ለማወቅ እንደማይቻል የሚናገሩት የአካባቢው ነዋሪዎች አስከሬን በየቦታው ወደቆ እንደሚታይ እየገለጹ ነው።
news
በዞኑ የሚኖሩ አንድ ታዋቂ ግለሰብ እንደተናገሩት ደግሞ ትናንት አርብቶ አደሮች ዲመካን በሌሊት ለመያዝ ጥቃት በፈጸሙበት ወቅት የመንግስት ወታደሮች ከባድ መሳሪያ በመተኮስ በወሰዱት የአጸፋ እርምጃ በመቶዎች የሚቆጠሩ ሰዎችእንደተገደሉ መረጃው እንደደረሳቸው ገልጸዋል። በሶስት ፒካፕ መኪኖች የተጫኑ ቁስለኛ ወታደሮች ጂንካ ሆስፒታል መግባታቸውንም አክለው ገልጸዋል። ሁለቱም ወገኖች ለወራት የጦርነት ዝግጅት ሲያደርጉ መቆየታቸውን የሚናገሩት ግለሰቡ፣ የችግሩ ምንጭ ከምርጫ ጋር ብቻ ሳይሆን ከመሬት ጋር የተያያዘ መሆኑም ይገልጻሉ።

ሌላ የአካባቢው ነዋሪም እንዲሁ በተወሰደው እርምጃ ከ100 በላይ ሰዎች መገደላቸውን መረጃ እንደደረሳቸው ተናግረዋል ። የወረዳው አስተዳዳሪ አቶ በርጤ ዢላ መግለጫ ለመስጠት ፈቃደኛ አለመሆናቸውን ተናግረዋል።
ኢሳት በሁለቱም ወገን የሞቱትን ሰዎች ከገለልተኛ ወገን ለማጣራት ያደረገው መኩራ አልተሳካለትም። ኢሳት ከሶስት ቀናት በፊት አርብቶአደሮች 3 ፖሊሶች ማቁሳለቸውን ዘግቦ የነበረ ሲሆን፣ ሆቴል ቤቶችና ሌሎች አገልግሎት ሰጪ ተቋማት አሁንም ድረስ እንደተዘጉ ነው።
ለወራት የዘለቀው ውጥረት ምርጫውን ሰበብ አድርጎ መጀመሩን ነዋሪዎች ይገልጻሉ። ሰመጉ ከሁለት ሳምንት በፊት ባወጣው ልዩ መግለጫ ከጥር 7 ቀን 2007 ዓ.ም ጀምሮ በተከሰተ ግጭት 7 ሰዎች መገደላቸውንና 9 ሰዎች መቁሳለቸውን በጥናት አረጋግጦ ይፋ አድርጓል።

ሰመጉ በሪፖርቱ ህዳር 7 ቀን 2007 ዓም አቶ ዑልዴ ሃይሳ በሐመር ወረዳ ሸንቆ ወልፎ ቀበሌ ውስጥ ነዋሪ የነበረ አርብቶ አደር ሲሆን፣ በድንገት በተነሣ አለመግባባት ምክንያት ባሌ ኢልዴ በተባለ የፖሊስ አባል ኩላሊቱ ላይ በከባድ እርግጫ በመመታቱ የአቶ ዑልዴ ህይወት በእለቱ ህዳር 7 አልፏል። የሐመር ብሔረሰብ አባላት አቶ ዑልዴን የገደለው የፖሊስ አባል ሕግ ፊት ቀርቦ ባለመጠየቁ ከፍተኛ ቅሬታ አድሮባቸውና የመበደል ስሜት ውስጥ ገብተው እንደነበር የሰብአዊ መብት ድርጅቱ አስታውቃል።

ማንጐ ተብሎ በሚጠራው ፓርክ ጎሽ የገደሉ የሐመር ብሔረሰብ አባላትን ለመያዝ ከደቡብ ኦሞ ዞን ፓሊስና ልዩ ኃይል የተውጣጡ አባላት ጥር 7/ 2007 ሥፍራው ሲደርሱ ለሽምግልና የተቀመጡ የአካባቢውን ሽማግሌዎች ጎሽ ገዳዮችን እንዲያወጡ በጠየቁዋቸው ጊዜ “በቅርቡ የተፈጸመውን የአቶ ዑልዴን ግድያ ሳታጣሩና ገዳዩን ይዛችሁ ለፍርድ ሳታቀርቡ፣ ከረዥም ጊዜ በፊት ጎሽ ገደለ የምትሉትን ሰው ለመያዝ እንዴት መጣችሁ?” የሚል ጥያቄ ማቅረባቸውን ይሁን እንጅ ” የፖሊስና ልዩ ኃይል አባላቱ በወቅቱ የተሰጣቸው ግዳጅ ጎሽ የገደለን ሰው መያዝ ብቻ መሆኑን በመግለጽ፣ ፖሊስ የተላክሁበትን ግዳጅ እፈጽማለሁ በማለቱ የሐመር ሽማግሌዎችና የማኅበረሰቡ አባላት ደግሞ የአቶ ዑልዴ ሃይሳን ገዳይ ሳትይዙ የጎሽ ገዳይ ልትይዙ አትችሉም በሚል አለመግባባት መፈጠሩን ሪፖርቱ ያስረዳል።

አለመግባባቱ እየተካረረ ሄዶ በዚያው ቀን ጥር 7 ቀን 2007 በሐመር ማኅበረሰብ አባላትና በፖሊሶች መካከል ተኩስ ተጀምሮ፣ ሰፋ ወዳለ ግጭት ያመራ ሲሆን በግጭቱም 7 ሰዎች ሲሞቱ 9 ሰዎች መቁሰላቸውን ማረጋገጡን የሰመጉ 134ኛ ሪፖርት ያስረዳል።

ሰመጉ ባወጣው የሟቾች ስም ዝርዝር አብዛኞቹ የሞቱትና የቆሰሉት የደቡብ ኦሞ ዞን ፖሊስና የልዩ ሃይል አባላት ናቸው።

ሰመጉ በግጭቱ ተሳታፊ ከነበሩት የሐመር ብሔረሰብ አባላት በኩል ምን ያህል ሰዎች ጉዳት እንደደረሰ ለማወቅ አለመቻሉን በመግለጫው አስታውቋል።
በሃመር ወረዳ ከ45 ሺ በላይ ነዋሪዎች ይኖራሉ። ዲመካ የወረዳው ዋና ከተማ ናት።

The post በሃመር ወረዳ ከፍተኛ እልቂት መድረሱን የአካባቢው ነዋሪዎች ገለጹ appeared first on Zehabesha Amharic.

ከመስፍን ወልደማርያም (ፕሮፍ) ምን እንማር? (ኤልያስ ገብሩ ጎዳና)

$
0
0
ጋዜጠኛ ኤልያስ ገብሩ

ጋዜጠኛ ኤልያስ ገብሩ

ሚያዚያ 16 ቀን 2007 ዓ.ም 85 ዓመት ለሆናቸው መስፍን ወልደማሪያም (ፕሮፌሰር)፣ ደጋግሞ ታላቅ ክብር መስጠት ተገቢ ነው ብዬ አምናለሁ፡፡ በዚህ ዕድሜ ስለሀገር እና ህዝብ የሚያምኑበትን፣ የሚታዘቡትን፣ የሚያዝኑበትን፣ የሚደሰቱበትን፣ …ሀሳብ መሰረት በማድረግ ብዕርን ከወረቀት ወይም ጣቶችን ከኮምፒውተር ኪቦርድ ጋር አገናኝቶ ለህትመት እና ለማኅበራዊ ድረ-ገጽ አንባቢያን ማቅረብ መቻል የሚያስመሰገን ተግባር ነው፡፡

ሀገራችን በተለያዩ የሙያ እና የዕውቀት ዘርፎች ያፈራቻቸው እጅግ በርካታ ምሁራኖች እንዳሏት ይታወቃል፡፡ ነገር ግን አብዛኞቹ፣ ሀገር እና ህዝብ (ከሚያውቁት አኳያ) ብዙ ሲጠብቅባቸው የጋን ውስጥ መብራት ሆነው፣ አይተው እንደላዩ፣ ሰምተው እንዳልሰሙ፣ ታዝበው እንዳልታዘቡ፣ አውቀው እንዳላወቁ በመሆን አንድም በፍርሃት አሊያም የሥርዓቱ አሸብሻቢ መሆንን መርጠው አድርባይነት መገለጫቸው ሆኗል፡፡ ይህ የሚያሳዝን አካሄድ ፕሮፍን አይመለከትም፡፡ ሥርዓቱ ተከፋ አልተከፋ፣ ተቆጣ አልተቆጣ፣ አሰረ አላሰረ፣ አስፈራራ አላስፈራራ ፕሮፍ ያመኑበትን በድፍረት ሲነገሩ እና ሲጽፉ ኖረዋል፡፡ ፈጣሪ ጤናና ዕድሜ ይስጣቸው፣ በዚህ መንገድ ዛሬም ነገም ይኖሩታል፡፡ ፕሮፍን ብዙ በጽሑፋቸው፣ ጥቂት በአካል ከማውቃቸው አኳያ፣ እንደዛሬ ትውልድ አባልነቴ ‹‹ከእሳቸው ብንማር ይጠቅሙናል›› ብዬ ከማስባቸው ነገሮች መካከል የተወሰኑትን ከዚህ በታች ልጥቀስ፡-

ተፈጥሮን መኖር
——
በዓለማችን ላሙኑበት ዓላማ፣ እስከመጨረሻው ድረስ ከመንገዳቸው ሳይዛነፉ የሚኖሩ ሰዎች ቁጥር አነስተኛ ይመስሉኛል [ጥናት ላይ የተመረኮዘ ጽሑፍ ስላልሆነ ነው]፡፡ ላመኑበት እውነት የሚኖሩ ሰዎች፣ በውስጣቸው የሚለዋወጥ ፍላጎት ሳይሆን ረግቶ የሚኖር መሻት አላቸው፡፡ ይህም ነው፣ በዋነኝነት ጽኑ የሚያደርጋቸው፡፡ በሁኔታዎች እና በጊዜያቶች የሚዋልል ፈላጎት ያላቸው ሰዎች ቆምንለት ላሉት ሀሳብ ሩቡን ወይም ገሚሱን እንኳን ሳይጓዙ ማሊያቸውን ለውጠው የመገለባበጥ ጅምናስቲክ ሲሰሩ ይገኛሉ፡፡ በሀገራችንም ቢሆን ይሄን ትናንት አይተናል፤ ዛሬም ሆነ ነገ እናይ ይሆናል፡፡ ከዚህ ረገድ፣ ፕሮፍ ካሏቸው ጽኑ መሻቶች መካከል አንዱ፤ በሀገራችን የሰብዓዊ መብት ተከብሮ ማየት መሆኑን ከተግባራዊ እንቅስቃሴዎቻቸው በቀላሉ ማየት ይቻላል፡፡ ሰመጉ ጥሩ ምሳሌ ነው፡፡ ፕሮፍ፣ ስለፍትህ መጓደል፣ ስለ ዴሞክራሲ ንፍገት፣ ስለነጻነት ዕጦት፣ ስለችጋር፣ ስለትውልዱ ችግር፣ …ወዘተ ያለመታከት ጽፈዋል፡፡ ይሄ እንግዲህ በሀገራችን የሚታዩ ወሳኝ ችግሮችን ለማጋለጥ ጠንክሮ መቆምን ያሳያል፡፡

እኔ እና አቤል አለማየሁ በ2005 ዓ.ም መጨረሻ ላይ በጋራ አዘጋጅተነው በነበረው ‹‹ኢትዮጵያን ማን ይታደጋት?›› መጽሐፍ ላይ እንዲህ ገልጸው ነበር፡- ‹‹የተፈጠርኩለትን ዓላማ ምን እንደሆነ በእውነት አላውቅም፡፡ [ፈገግታ ያጀበው ሳቅ] በአዕምሮህ ‹ይህ ተፈጥሮዬ ነው› ልትል ትችላለህ፡፡ አዕምሮህን ስለህ፣ እያሰብኩ ‹ይሄ ትክክለኛ መንገድ ነው፤ በአስተሳሰብ፣ በሕግ ሀልዮት ደረጃ ይሄ ትክክል ነው› ብለህ የምትሄድበት መንገድ አንዱ ነው፡፡ ሁለተኛ ደግሞ በልብህ፣ በህሊናህና በስሜትህ መጥፎ፣ ክፉ ነገር ስታይ ያን መጥላትህ፣ ‹‹እንደዚህ ዓይነት ነገር በሰው ላይ መፈጸም የለበትም›› ብለህ ራስህን አጋልጠህ መኖርህ፣ ሐሳብ እና ስሜትህ በተገናኙበት መንገድ ለመሄድ መቻልህ ተፈጥሮዬ ነው ልትል ትችላለህ፡፡ እምነትም እዚህ ውስጥ ሊገባ ይችላል፡፡ ራስህን ብቻ አውጥተህ፣ ጥቅም ብቻ እያሳደድክ የምትኖረው ኑሮ ለእኔ በፍጹም ሕይወት አይደለም፡፡ በአከባቢዬ ያለው፣ በመስኮት ስመለከት የማየው ነገር ሁሉ እንዲነካኝ፤ የሌላው ችግር እንዲቸግረኝ፣ የሌላው ሰቆቃ እና ጭቆና እንዲሰማኝ እፈልጋለሁ፡፡ የሰውየውን ያህል ችግሩ ላይሰማኝ ቢችልም ትንሽም ቢሆን እንዲነካኝ ካላደረኩኝ ለእኔ ሕይወት ምንም ትርጉም የለውም፡፡›› በዚህ ገለጻ ውስጥ፣ በተፈጥሮ መንገዳቸው መሄዳቸውን እና ለሰብዓዊነት ተቆርቋሪነታቸውን በግልጽ መረዳት ይቻላል፡፡

ድፍረት
—–
በሕይወት፣ የሚያምኑበትን ነገር መለየት እና ለተግባራዊነቱ መወሰን፣ መንቀሳቀስ መጀመርና ላመኑበት ነገር መኖር ድፍረትን ይጠይቃል፡፡ በአጭሩ ፕሮፍን ድፍረት ይገልጻቸዋል፡፡ ያመኑበትን በግልጽ አማርኛ ይናገራሉ፡፡ ይሄንን ለመረዳት እና ለማረጋጋጥ የጻፏቸውን መጽሐፎች፣ ግጥሞች፣ ግለ-ሀሳቦች መለስ ብሎ ማየት ነው፡፡ ከላይ በተጠቀሰው መጽሐፍ ውስጥ፣ በፍርሀት ቆፈን ውስጥ ስላሉ ሰዎች ሀሳብ እንዲሰጡን ለፕሮፍ ጥያቄ እንስቼላቸው፣ እንዲህ ብለዋል፡- ‹‹ፍርሃቱን ልትነግረው ‹‹ተው አትፍራ›› ብትለው አትችልም፤ የማይቻል ነው፡፡ ፍርሃት በጣም የግል (Subjective) ነው፡፡

ፍርሃቱ እስኪተውው ድረስ ‹‹አትፍራ›› ልትለው አትችልም፡፡ አንተ ባለመፍራት አንዳንድ ነገር ስታደርግ እሱ ስለሚፈራ ‹‹ቂል›› ይልህ ይሆናል፡፡ ፈሪ ሆኖ ጥሩ ፎቅ ቤት ውስጥ ይኖራል፡፡ ጥሩ ኑሮ ይሆናል፡፡ አንተ ያልሆነ አልባሌ፣ ዓይነት ኑሮ በመኖርህ ‹‹ይሄ ቂል አርፎ ቢቀመጥ፣ እንደ እኔ እንዲህ መኖር ይችል ነበር›› ይልሃል፡፡ ይሄን መቻል አለብህ፡፡ ነገ፣ ከነገወዲያ፣ ሁልጊዜ በአንድ መስመር እንድትሄድ የሚደርግህ እንዳልኩህ ሚዛንህን መያዝህ ነው፡፡›› የዛሬ ወር ገደማ ፕሮፍ በማኅበራዊ ድረ-ገጽ (በፌስ ቡካቸው) ላይ ባሰፈሩት አጭር ጽሑፋቸው ውስጥ ኑሯቸውም ሆነ ሞታቸውም በሀገራቸው መሆኑን አጽንኦት በመስጠት ሀገር ጥለው እንዲወጡ እየተነኳኮሷቸው ላሉት ካድሬዎች የሰጡት አጭር ምላሽ በድፍረት የታጀበ ነበር፡፡ በዚህ አጋጣሚ በቤታቸው የሚገኙት የገብረ-ክርስቶስ ደስታ ስዕሎች መሆናቸውን ጠቅሰው ‹‹በዚህ አጋጣሚ ሥዕሎቹን የሚገዛ…›› ያሏት አገላለጽ ደስ እና ፈገግ አስደርጋኛለች፡፡

አድናቆት እና ትችትን መቻል
——-
ለፕሮፍ የተለያዩ ሰዎች በተለያዩ ጊዜያት አድናቆትን በቃላትና በጽሑፍ ሰጥተዋቸው ያውቃሉ፡፡እንዲሁም ፕሮፍ በጋዜጦች/በመጽሔቶች/በመጽሐፎቻቸው ባነሷቸው ሀሳቦች ላይ ተንተርሰው የተለያዩ ሰዎች ትችትን በጽሑፍ አቅርበውባቸውም አንብበናል፡፡ ለተቿቸው ሁሉ ግን መልስ አይሰጡም፡፡ ምሳሌ ለማንሳት ያህል፣ ‹‹መክሸፍ እንደኢትዮጵያ ታሪክ›› ለተሰኘው አነጋጋሪ መጽሐፋቸው ዲያቆን ዳንኤል ክብረት ላነሳባቸው ትችት መልስ ሰጥተውታል፡፡ የኢዴፓ አመራር የነበረው አብዱራህማን መሐመድ በሰንደቅ ጋዜጣ ላይ ሰፊ ጽሑፍ ፕሮፍ ላይ ቢጽፍም አጸፋዊ መልስ ነፍገውታል፡፡ ስለዚህ ፕሮፍ መልስ የሚሰጡበትና የማይሰጡበት የትችት ዓይነት እንዲሁም ሰዎች ስለመኖራቸው የሚያሳይ ነው፡፡ እሳቸው ቢሆኑ አድናቆቱም ሆነ ትችቱ አልጣላቸውም፡፡ እዚህ ጋር፣ ‹‹አድናቆት ይጥላል ወይ?›› የሚል ጥያቄ ሊነሳ ይችል ይሆናል፡፡ መልሴ አዎን ነው፡፡ አድናቆትን መቆጣጠር የሚችሉ ሰዎች እንዳሉ ሁሉ፤ በአድናቆት ሰክረው ከመንገዳቸው የሚንሸራተቱ ሰዎች መኖራቸውን ማወቅም ተገቢ ነው፡፡ በትችት መንፈሳቸው በቀላሉ የሚሰበሩ ሰዎች አሉ፤ አይተናልም፡፡ ፕሮፍም ቢሆኑ ለሰዎች አድናቆት ሲሰጡ እና ጠንካራ ትችትን ሲሰነዝሩም እናውቃቸዋለን፡፡ አንድ ሰው ራሱን አደባባይ ላይ በተለያየ መንገድ አውጥቶ ልተች አይገባም ሊል እንደማይችል በአንድ ወቅት ከሰጡት ቃለ-ምልልስ ተረድቻለሁ፡፡ ስለዚህ አድናቆትንም ሆነ ትችትን መቻል ትልቅ ጥበብ አድርጎ መውሰድ ይቻላል፡

ተስፋ አለመቁረጥ
—–
በሀገራችን የፖለቲካው መስክ፣ ይበልጥ የተስፋ የመቁረጥ አዝማሚያ በብዙዎች ላይ በገሃድ ይንጸባረቃል፡፡ አፍ አውጥተው ተስፋ መቁረጣቸውን የሚናገሩም አሉ፡፡ ይህ የተስፋ መቁረጥ ስሜት በተለይ ወጣቶች ላይ ሲታይ ያስጨንቃል፤ ያሳዝናልም፡፡ ለሥርዓቱ የጭካኔ በትር በአንድ ጊዜ የሚንበረከኩ ሰዎች መኖራቸውንም በግል ታዝቤያለሁ፡፡ ይህ የተስፋ መቁረጥ ስሜት ‹‹መስመራችን ነው›› ካሉት ጎዳና አስወጥቶ እስከወዲያኛው ያርቃቸዋል፡፡ ከዚያም አይተው እንዳላዩ፣ ሰምተው እንዳልሰሙ፣ አውቀው እንዳላወቁ ወደመሆን ያመራሉ፡፡

ፕሮፍ ግን፣ ሀገሪቷ በተለያዩ አስቸጋሪ ሁነት ውስጥ እየኖረች መሆኑን ተገንዝበው፤ አይተው እንዳላዩ፣ ሰምተው እንዳልሰሙ፣ አውቀው እንዳላወቁ መሆን አልቻሉም፡፡ ባለፈው ዓመት መጨረሻ አካባቢ ‹‹ፋክት›› መጽሔት ከመዘጋቷ በፊት በየመጽሔቷ አምደኛ ሆነው በየሳምንቱ ሀሳባቸውን ይሰነዝሩ ነበር፡፡ ከዚያ በኋላም ቢሆን፣ በማኅበራዊ ድረ-ገጽ በፌስ ቡክ ገጻቸው አልፎ አልፎም ቢሆን ሃሳባቸውን እየጻፉ ማስነበባቸውን ቀጥለዋል፡ች በሀገራችን ብዙ አሳዛኝ ድርጊቶች መፈጸማቸው ቀጥለዋል፡፡ በእነዚህ አሳዛኝ ሆነቶች ፕሮፍ ተስፋ ቢቆርጡ ኖሮ ሀሳባቸውን በአንድም ይሆን በሌላ መንገድ ባላየን ነበር፡፡ ይህ፣ በሀገር ጉዳይ ተስፋ ያለመቁረጥ ስሜት አንዱ ማሳያ ነው፡፡ ተስፋ ስንቆርጥ እንቅስቃሴያችን ይገታል፡፡ ስለዚህ፣ ሰዎች በሕይወት እስካለን ድረስ ተስፈኛ መሆን ይገባናል፡፡

እንግዲህ በግሌ ከፕሮፍ ብንማራቸው ይጠቅሙናል ያልኳቸውን እራት ነጥቦች በአጭሩ ለማቅረብ ጥረት አድርጌያለሁ፡፡ ሌሎችም ፕሮፍን ከማወቅ አኳያ፣ አስተማሪ ናቸው የምትሏቸው ሀሳቦች ካሉ ሀሳባችሁን ሰንዝሩና አብረን እንማማር፡፡

(በዘንድሮው የፋሲካ ዕለት፣ ሚያዚያ 4 ቀን 2007 ዓ.ም የተጻፈ)

በዚህ አጋጣሚ፣ ፈጣሪ ዕድሜ እና ጤናን ለፕሮፍ ይስጥ ብያለሁ!

ቸር እንሰንብት!

The post ከመስፍን ወልደማርያም (ፕሮፍ) ምን እንማር? (ኤልያስ ገብሩ ጎዳና) appeared first on Zehabesha Amharic.

“ሁሉም ሰው ከብሔሩ ወይም ከሰፈሩ ይልቅ ለኢትዮጵያዊነቱ ቅድሚያ ቢሰጥ ሀገራችን ታድጋለች” ዳዊት ፍሬው ኃይሉ

$
0
0
“ሁሉም ሰው ከብሔሩ ወይም ከሰፈሩ ይልቅ ለኢትዮጵያዊነቱ ቅድሚያ ቢሰጥ ሀገራችን ታድጋለች” ዳዊት ፍሬው ኃይሉ

“ሁሉም ሰው ከብሔሩ ወይም ከሰፈሩ ይልቅ ለኢትዮጵያዊነቱ ቅድሚያ ቢሰጥ ሀገራችን ታድጋለች”
ዳዊት ፍሬው ኃይሉ

ትዕግስት ታደለ

የአንጋፋው ድምጻዊ የፍሬው ሀይሉ ልጅ ነው፡፡ የአባታቸውንን ፈለግ ተከትለው ወደ ሙዚቃ ዓለም ከተቀላቀሉ የአንጋፋ ሙዚቀኛ ልጆች መሀከል የተሳካለት የክላርኔት ተጫዋች አንዱ የሆነው ዳዊት ፍሬው ኃይሉ በሙዚቃ መሳሪያ ብቻ የተቀነባበሩ ሁለት ሲዲዎችን ለእድማጭ አቅርኋዋል፡ ፡የሙዚቃ ትምህርቱንም በያሬድ ሙዚቃ ት/ቤት ተምሯል፡፡ ‹የሰው ልጅ በአብዛኛውን በምሳ ሰዓትም ሆነ ማታ ወደ እንቅልፉ የሚሄደው በሙዚቃ መሳሪያ ብቻ በተቀነባባሩ ሙዚቃዎችን እየሰማ ነው፡፡› የሚለው ዳዊት እስካሁን በሰራሁት ስራ የሚገባኝን ያህል ገቢ አግኝቻለሁ ለማለት ባልችልም ሲዲዬን ገዝቶ ያዳመጠ ሰው ግን ነፍሱን አስደስቷል ብዬ አምናለሁ› ይላል፡፡እኛም የመሿለኪያ አምዳችን እንግዳ አድርገነው እንዲህ አውግቶናል፡፡

ቁም ነገር፡- የደስታና የሐዘንን ስሜት አውጥቶ ከመግለጽና ተቆጣጥሮ ከማለፍ የትኛው ይሻላል?

ዳዊት፡- ሁለቱም ስሜቶች መደበቅ የለባቸውም፤ ግን ደስታ ላይ ገደብ ሊኖረው ይገባል፣ ሐዘንም ላይ እንዲሁ ገደብ ሊኖረው ይገባል፡፡ ሲለቀስም አልቅሰው ሲመጣላቸው ፤ሲደሰቱም መደነስ የሚችለው ደንሶ፣ መጨፈር የሚችለውም ጨፍሮ ጨፍሮ ሲወጣለት ደስ ይላል፡፡ ድብቅ መሆንን አልደግፍም፡፡

ቁም ነገር፡- የአንድ ደቂቃ የህሊና ፀሎት ሲባል ወደ አዕምሮህ ምንድን ነው የሚመጣው?

ዳዊት፡- እኔ የአንድ ደቂቃ የህሊና ፀሎትን ሳስብ መድረክ መሪዎቹ ላይ ነው የማዝነው፤ የአንድ ደቂቃ የህሊና ፀሎት እናድርግ ይባልና ሰውን አስነስተው ማስቀመጣቸውን እንጂ የሚያዩት በትክክል ደቂቃውን አያዩትም፡፡ የአንድ ደቂቃ የሚሰጠው ሰው እዛ ጋር ቁሞ ሀሳብን ሰብስቦ ጸሎት የሚደረግለትን ስው ለማሰብ ነው፡፡ እነሱ ግን አስራ አምስተኛው ሰኮንድ ላይ ተቀመጡ ይላሉ፤ ያ ይረብሻል፡፡ መድረክ መሪዎቹ ይህን የሚያደርጉት ዝም ብለው ለፎርማሊቲ ነው፡፡ እኔ ግን አዕምሮዬ ውስጥ የሚመጣው ያረፈውን ሰው ነፍስ በገነት ያኑርልኝ የሚለው ነው፡፡

ዳዊት፡- እንግዲህ እኔ ፍቅር ይዞኝ ያውቃል፤ የእውነተኛ ፍቅር ምክንያታዊ ነው፡፡ ወይ በአይንሽ በምታይው ነገር ተማርከሽ አለበለዚያ በተግባር ከምታየው ባህሪ ሊሆን ይችላል፤ በምክንያት ነው ፍቅር የሚዝሽ እንጂ ምክንያታዊ

ሳይሆን ፍቅር አይኖርም፡፡ ፍቅር ፈጣን ሎተሪ አይደል /ሳቅ/

ቁም ነገር፡- የዛሬ መቶ አመት ኢትዮጵያ በአንተ አመለካከት ምን አይት ገጽታ የሚኖራት ይመስልሃል?

ዳዊት፡- የዛሬ መቶ ዓመት በጣም ረጅም ጊዜ ነው፡፡ ምን ትሆናለች?

የሚለውን ሳይሆን የኔን ምኞት ብናገር ይሻለኛል፡፡ ምክንያቱም መገመት ይከብዳል፤ የዛሬ መቶ ዓመት የእኔ ምኞት የአፍሪካ ዋና ከተማ ሳይሆን የዓለም ዋና ከተማ እንድትሆን ነው፡፡ በአይናችን የምናያቸው ነገሮች አሉ የሚካድ ነገር አይደለም፤ ይሄ ነገር በመቶ ሳይሆን በመቶ ሺህ ተባዝቶ ተባዝቶ ሰዉ የሚሰጥ

እንጂ የሚቀበል እንዳይሆን እመኛለሁ፡፡

ቁም ነገር፡- ፖለቲካና ኮረንቲ በሩቅ ለምንድን ነው የሚባለው?

ዳዊት፡- ይሄ የአስተሳሰብ ጉዳይ ነው፡፡ ያው እንግዲህ ሰው መኖርን ስለሚፈልግ ፖለቲካው ለመጥፊያው ምክንያት እንዳይሆንበት ከመፍራት ነው፡፡ ኤሌክትሪክ የሚሸሸው እንዳያጠፋን ነው አይደል፤ ፖለቲካም ለመጥፊያችን ምክንያት እንዳይሆን ነው፡፡

ቁም ነገር፡- ሙዚቃ ባይኖር ኖሮ የሰው ልጅ ህይወት ምን ይመስል ነበር?

ዳዊት፡- በሙዚቃ እኮ ነው ስሜት የሚገለፀው፤ ዓለም ጎዶሎ የምትሆን ነውየሚመስለኝ፡፡ሙዚቃባይኖርሰውደስሲለውሲያዝንስሜቱንየሚገልጽበት ያጣል፡፡ በንግግር ከሚነገረው መልዕክት እኮ በዜማ የሚሰማው መልዕክት ብቃቱ የትየለሌ ነው፡፡ አሁን የጥላሁን ‹‹ዳግመኛ ቢፈጥረው›› ዘፈን ስትሰሚ ሰው ደጋግሞ በንግግር ከሚነግርሽ ሁለቷን የጥላሁንን ስንኝ

‹‹ሞት እንኳን ጨክኖ ወስዶ ከሚያስቀረው››
‹‹ምናለ ደጋጉን ዳግመኛ ቢፈጥረው›› የሚለውን በዜማ ብትሰሚ

ትልቅ ጉልበት አለው፡፡ ሙዚቃ ሁሉ ነገራችን ውስጥ አለ፡፡ ሲሸለል ሲፎከር ሁሉ ሙዚቃ አለ፤ ስለዚህ ሙዚቃ ባይኖር ብዙ ነገር ይጎልብናል፡፡ ሙዚቃ የዓለም የልብ ምት ነች፡፡

ቁም ነገር፡- በሰው በሀገራት ስም የሚጠሩ የከተማችን ሰፈሮች የትኞቹን ታውቃለህ?
ዳዊት፡- ሪቼ የሚባል አለ አይደል? ሪቼ የሰው ሀገር ስም ነው እንዴ? እኔ ምን እንደሆነም አላውቅም፤ የሰው ሀገር ስም ይመስላል /ሳቅ/፤ ካሳንችስ ምንድን ነው? ምናልባት ሩዋንዳ የሚለው በሰው ሀገር ስም ነው መሰለኝ /እ…. እንደማሰብ / እንግዲህ የሩዋንዳው ብቻ ነው የመጣልኝ፡፡

ቁም ነገር፡- መጋኛ ምንድን ነው?

ዳዊት፡- መጋኛ የሰይጣን ታናሽ ወንድም ይመስለኛል፡፡ በፊት ጠዋት ላይ ሆዴን ይቆርጠኝ ነበረ፤ ስጠይቅ በር ከፍተህ ስለወጣህ ነው፡፡ መጋኛ መቶህ ነው ይሉኛል፡፡ ቁርጠት ነው በሽታ ያመጣብኝ፣ በሽታ ደግሞ ሰይጣን ነው፡፡ ስለዚህ

መጋኛ የሰይጣን ታናሽ ወንድም ነው ወይም ደግሞ የሰፈሩ ልጅ /ሣቅ/ ፡፡

ቁም ነገር፡- ስዕል ፣ ሙዚቃ፣ ቴአትር እና ፊልም ከነዚህ ላንተ የትኛው ነው ህይወትን በደንብ የሚገልፅልህ? ለምን?

ዳዊት፡- ሙዚቃ ጉልበት አለው፡፡ እኔ ሙዚቀኛ ስሆንኩ አይደለም፤ አንዳንድ ጊዜ የኛ ያልሆኑ ሙዚቃዎችን ከፍቼ ሳዳምጥ የማላውቀው ቦታ ይዞኝ ይሄዳል ፣ የሚፈጥረው ስሜት አለው፡፡ ለዚህ ነው ሙዚቃ የአለም ቋንቋ ነው የሚባለው፤ አሁን ለምሳሌ የቻይና ሙዚቃ ብንሰማው የማናውቀውን ዓለም ነው የሚያሳየን፡፡ ቋንቋውን የማናውቀውን ፊልም ወይም ቴአትር ብናይ ግን ዝም ብለን ምስሉን፣ እንቀስቃሴውን እናያለን እንጂ አይገባንም፡፡ ሙዚቃ ግን ኖታ ነው፡፡ ስትሰሚው ሌላ ዓለም ይዞሽ

ይሄዳል፡፡ቁም ነገር፡- ጫማው ከጠበበው ሰው እና ሽንቱ ከወጠረው ሰው የትኛው ይሻላል?

ዳዊት፡- እንዴ ጫማው የጠበበው ሰው ነዋ! የሚሻለው /ሣቅ/ ፤ጫማው የጠበበው ሰው ምን ቢጠበውም እግሩ አይቆረጥም ምንም አይሆንም ፡፡ሽንቱ የወጠረው ሰው ግን መንገድ ላይ ቢሆን የወጠረው ምን እንደሚፈጠር ማወቅ

አያዳግትም፡፡ በተፈጥሮ መያዝና በሰው ሰራሽ መያዝ ምን አንድ አደረገው /ሣቅ/፡፡

ቁም ነገር፡- ሀገራችን ከድህነት በቀላሉ መላቀቅ ያልቻለችው ለምንድን ይመስልሃል?

ዳዊት፡- ይህ እንግዲህ ሰፊ ነው ጉዳዩ ፤አንደኛ መናበብ ካለመቻል ነው፡ ፡ ሁሉም ሰው ከብሔሩ ወይም ከሰፈሩ ይልቅ ለኢትዮጵያዊነቱ ቅድሚያ ቢሰጥ

ሀገራችን ታድጋለች፡፡ ችግሮችና ቢኖሩም ሁሌም ማስቀደም ያለብን ኢትዮጵያን ነው፡

፡ በዚህ ምክንያት ይመስለኛል፡፡

ቁም ነገር፡- በአሁኑ ወቅት የወጣቱ አንገብጋቢ ጥያቄ ምንድን ነው ትላለህ?

ዳዊት፡- ለስራ የተዘጋጀ ስነ ልቦና አለመኖር ይመስለኛል፤ ለስራ ዝግጁ

አለመሆን ነው፡፡ አንዳንድ ጊዜ ባህላችን ሆኖ የበታችነትን እንጠላለን፤ አንድ ሰው

ራሱንበአካዳሚዕውቀትሳያዳብርሥራአጣሁብሎቢያወራምንይገርማል፡፡ ለስራ

ዝግጁ አለመሆን ይመስለኛል አንገብጋቢው ነገር፡፡

ቁም ነገር፡- ነገረኛ ጎረቤት ምን አይነት ነው?

ዳዊት ፡- ምነሻ ሃሳብ የሚፈልግ ነዋ ! /ሳቅ../ ሙዚቃ እንኳን ብትከፍቺ

ከቀኑ አምስት ሰዓት ላይ አረ ድምጹን ቀንሱ እንተኛበት የሚል! ያው አንዳንዴ

ትደበሪበታለሽ! የሚለውን እየሰማሽ! እንደዚህ ነው ከልምዴ የማቀው፡፡

ቁምነገር ፡- አመሰግናለሁ፡፡

The post “ሁሉም ሰው ከብሔሩ ወይም ከሰፈሩ ይልቅ ለኢትዮጵያዊነቱ ቅድሚያ ቢሰጥ ሀገራችን ታድጋለች” ዳዊት ፍሬው ኃይሉ appeared first on Zehabesha Amharic.


“አማዉቱና!” አሙዋሙቱን (አብረን እንሙት) ሠናይ ገብረመድህን ዮሀንስ (ጋዜጠኛ)

$
0
0

ሰናይ ገ/መድህን

ኤርትራዊያኖች አማዉቱና ብለዉ የሰየሙት ታሪክ አላቸዉ፡፡ኤርትራ ነፃ አገር ከሆነች በሁዋላ የአፍላነት ወግን የወረሰዉ የአዲሱ ትዉልድ ታሪክ ነዉ፡፡ የብሄራዊ አገልግሎት አባላት ታሪክ፡፡ እንዲህ ነዉ፡፡

ህግሓኤ መላዋን ኤርትራ ተቆጣጥሮ ጊዚያዊ መንግስትነቱን ካወጀ በሁዋላ (ለነገሩ አሁንም ከሀያ ሶስት ዓመት በሁዋላም ጊዚያዊ ነዉ የሚባለዉ) ከመጀመሪዎቹ አዋጆች የብሄራዊ ዉትድርና አገልግሎት አዋጅ ነዉ፡፡( ያገሩን ወጣት ሁሉ ለመሸከፍ ምን አጣደፈዉ ግን ወገኖቼ;! የሚሰጋበት ነገር ወይንም ያሰበዉ ነገር ነበረዉ፡፡) ሆነናም እነዚያ አፍላ ወጣቶች በነፃነትን ዘፈን ጨፍረዉ ሳይጠግቡና የአገሪቱን የወደፊት የፖለቲካ ኢኮኖሚና ማህበራዊ ጉዞ ሳይመላከቱ በህግሐኤ ማርቼዲስ
ሸዊት እየተጫኑ ወደ ሳዋ ወረዱ፡፡ ጫካ መነጠሩ የበረሀን የሰራዊት ኑሮ ጀመሩ፡፡ (ብታምኑም ባታምኑም ብሄራዊ አገልግሎት ተብለዉ ወርደዉ መመለሻዉና መሹለኪያዉ ጠፍቶባቸዉ ደንዝዘዉ በዉትድርና ሀያኛ ዓመታቸዉን የደፈኑ አሉ፡፡ አንዱ የአጎቴ ልጅ ነዉ፡፡ ከአንደኛ ዙር! ጀምሮ እስካሁኑዋ ሰዓት ከስር ከስር የሚተካዉን አገልግሎትማ ቤቱ ይቁጠረዉ፡፡10ሺ ከወረደ ግማሹ እግሩ ወደ መራዉ አገሪቱን ጥሎ ይሰደዳል ቀሪዉ እዛዉ ይገላበጣል፡፡ ከቀናዉ ቤቱ ሄዶ በዛዉ ይቀራል፡፡ በአፈሳ አስኪያዝ፡፡ ታዲያ ሳዋ መግቢያዉ ሰፊ መዉጫዉ እንደመርፌ ቀዳዳ ጠባብ ነዉና ሲወርዱ መቼ እንደሚመለሱ ስለማያዉቁ የስንብቱ ነገር አይጣል ነዉ፡፡ በዚህ ጠንቅ ነዉ ሲጠፉም ለሞት ደንታም የሌላቸዉ፡፡ እነሆ የባህር ዓሳ እራት የሚሆኑት በየበረሀዉ ወድቀዉ የሚቀሩት ከኢትዮጵያዉያን ወገኖቻችን ጎን በአረመኔዎች ቢላዋ እንደ በግ የታረዱት፡፡ ከፊት ሞት ከሁዋላ ሞት መሆኑን ካወቁ ሰነበቱና ፡፡ አሁን ሰላሳኛ ዙር አልፉዋል መሰል;) አጃኢብ !
ethiopia-eritrea-war-375x251
የመጀመሪያዎቹ ብሄራዊ አገልግሎት ወጣቶች ታዲያ ያልጠበቁት ነገር ነበር የገጠማቸዉ፡፡ ከነፃነት በሁዋላ የጥይት ድምፅ አይሰማባትም የተባለችዉ ኤርትራ ሸማቂ ታጣቂዎች ወጣ ገባ ማለት መጀመራቸዉ በመሰማቱ ፡፡እፎይታ ለናፈቀዉ የኤርትራ ህዝብ ሁኔታዉ አስደንጋጭ ነበር፡፡ ከወደ ሱዳን ድንበር በኩል መሆኑ ደግሞ ያልተጠበቀም ይመስላል ፡፡ የሆነ ሆኖ ከስልጠና በሁዋላ አብዘኛዎቹ ወጣቶች ወደ ዳግመ ግንባታና ሰላማዊ አገልግሎት ግዳጅ ፈፅመን በዚሁ ተገላግለን እንመለሳለን ያሉት ወጣቶች ከሽምቅ ተዋጊዎቹ ጋር ሊፋጠጡ ግድ ሆነ፡፡ አንዳችም የጦርነት ልምድ ባይኖራቸዉም እስኪ እጃቸዉን በዚህ ያሙዋሹ ብሎ የተፈረደባቸዉም ያስመስላል፡፡ በቃ የድንበር ጥበቃ ላይ ተሰማሩ እጃቸዉ ከቃታ ዋለና ወደ ሱዳን አማተሩ፡፡ መስዋዕትነትን ለመክፈልም ዝግጁ !፡፡

ይህ አልፎ አልፎ የተሰነዘረዉ የሸማቂዎቹ ጥቃትና ሰዶ ማሳደድ ዉጊያ የኤርትራዊንን ህይወት እንደገና መቅጠፍ ጀመረ፡፡ ያልተጠበቀዉ መስዋዕትነት ሌላላም አስገራሚ ሁኔታን አስከተለ፡፡፡ ይሄዉም በተለያዩ አጋጣሚዎች በታጣቂዎቹ ከተገደሉት ኤርትራዊያን የሰራዊት አባላት መካከል አብዛኛዎቹ ታጋዮች የመሆናቸዉ ጉዳይ፡፡ እንዲሁም ሸማቂዎቹ ወጣት ብሄራዊ አገልግሎቶችን አይገደሉም የሚገድሉት ታጋዮችን ብቻ ነዉ የሚለዉ ወሬ መናፈስ ያዘ፡፡ እንዲህ ዓነት አጋጣሚም ደርሱዋል ይባልም ጀመር፡፡ እንደሚታወቀዉ የኤርትራ መከላከያ ሰራዊት በነባር ታጋዮችና ወጣት ብሄራዊ አገልግሎት አባላት የተዋቀረ ነዉ፡፡ ሸማቂዎቹ ከዚህ ሰራዊት ዉስጥ ታጋዮችን ብቻ እየመረጡ የመግደላቸዉ ሁኔታ በርግጥም ታጋይ ሀላፊዎችን በጣም ያሳሰበና ያበሳጨ እንደሚሆን መገመት ይቻላል፡፡ ታጋይም ይሁን አገልግሎት እንዲሰዋበት ለማይፈልገዉ የኤርትራ ህዝብ ደግሞ ሰቀቀን መሆኑ አይታበልም፡፡ሁለቱም ልጆቹ ናቸዉና፡፡ ሸማቂዎቹ ታጋዮችን ብቻ ነጥለዉ ለምን ይገድላሉ; ለሚለዉ ጥያቄ ምላሹን ለነሱ እንተወዉ፡፡ ለመሆኑ በዉጊያ መሀልስ ወይንም በደፈጣ ታጋዮችን እንዴት መለየት ቻሉ? የኤርትራ ታጋዮች ሀላፊዎች ቁጭ ብለዉ መከሩ; እናም በቀላሉ ደረሱበት፡፡ የታጋዮቹና ብሄራዊ አገልግሎቶቹ ወታደራዊ ልብስ ቀለም የተለያየ ነበር፡፡ አስቸኩዋይ የዉሳኔ ሀሳብ አስተላለፉ፡፡ ከጥቂት ወራት በሁዋላ ለጥቃት የተሰማሩት ሸማቂዎች ታጋዮችን መለየት አልቻሉም፡፡ ምክንያቱም የኤርትራ መከላከያ ሰራዊት አባላት ታጋዮችም ብሄራዊ አገልግሎቶችም አንድ ዓይነት ወታደራዊ ልብስ መልበስ ጀምረዉ ነበርና ነዉ፡፡እናም ሸማቂዎቹ በጅምላ ጥቃት ለመሰንዘር ተሰማሩ፡፡ የተተኮሰ ጥይት ደግሞ ለይቶ አይገድልምና ሁሉም ለጥቃቱ ሊጋለጡ ግድ ሆነ፡፡ ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ብሄራዊ አገልግሎቶች ያን ወታደራዊ ዩኒፎርም ‹ አማዉቱና › ሲሉ ሰየሙት፡፡c

ማያያዣ አቦይ ተስፎም ይባላሉ፡፡ እኚህን ሰዉ ሁሉም ኤርትራዊ ያዉቃቸዋል፡፡ ሀያ ሶስት ዓመት ሙሉ ባገኙት አጋጣሚ ሁሉ ሲዋሹ ያዉቃቸዋል፡፡ ከሰማይ መና ይወርድልሀል ከሚለዉ የዳቦ ዘመን ዉሸት በቀር ስለ ህገመንግሰት ምርጫ ዲሞክራሲ ልማት ብልፅግና እድገት ሰላም ዳጎስ ያለ ደሞዝ …. ስጥ እንግዲህ በሉት ወይንም ረግጠዉታል፡፡ ዓይናቸዉን በጨዉ አጥበዉ በየጊዜዉ እንዳዲስ ይተረተራሉ፡፡ ረገጣዉ ኤርትራዊያንን ብቻ አይደለም፡፡ ኤርትራ ገብተዉ የወንድ በር መዉጫ ላጡና እንዲገቡ ለሚፈልጉዋቸዉ ኢትዮጵያዉያን ሁሉ ነዉ፡፡ታዲያ ፊዳ ሊያደርጉ ያሰቡትን ሲረግጡ ምን ደስ እንደሚለዉ ቀድመዉ አጥንተዉ በሳቸዉ የጨዋ ቁዋንቀዋ ይተረተራሉ፡፡ ዉስጣቸዉ ባያምንበትም ፊዳቸዉን ለመጣል ሲሉ ይምላሉ ይገዘታሉ፡፡ይሄዉ አሁን ከኢትዮጵያዉያን ጋር ስለ ኢትዮጵያ አንድነት ተሙዋጋች ሆነዉ የለ! የእሳቸዉ ባይገርመንም ከእኚህ የዲሞክራሲ ሾተላይ ሰዉ ጋር ማዕድ እየተቁዋረሱ ከበሮ እየደለቁ ያሉት ወገኖቻችን ጉዳይ ግን አጃኢብ ብቻ አሰኝቶ ዝም አላሰኘንም! ጎበዝ ሹምባሽነት ሲለምድ ደግ አይደለም፡፡ እናም እኚህን ልብ አዉልቅና የህዝብ ጦስ (ለቃሉ ይቅርታ) ኤርትራዉያን አቦይ ተስፎም ( አቦይ ተስፋይ ) !! ሲሉ ስም አወጡላቸዉና እዚያዉ በጠበልህ ሞኝህን ፈልግ አሉና ረግመዉ ከነበሩበት የክብር ቦታ አዉልቀዉ ወረወሩዋቸዉ፡፡አንዳንድ ኢትዮጵያዉያንን ግን አሁንም ማማለል ብሎም ማጃጃል ቀጥለዋል፡፡ ጉድጉዋቸዉ የተማሰዉ ልጣቸዉ የተራሰዉ እሳቸዉ ኢሳያስ አፈወርቂ !
‹ አማዉቱና !›
እኚህ አዛዉንት አሁንም ግድብ እያሰሩ ነዉ አሉ! ወይንም በቅርብ አመራር እየሰጡ ነዉ ፡፡ ሙያተኛ ስለማያምኑ ይሆን ; አዎና 23 ዓመት ሙሉ እየነደፉ እየቀየሱ ቆመዉ ያሰሩዋቸዉ( (እሳቸዉ የሁሉም ሙያ ባለቤት ናቸዉና) የገርሰት ግድብ፡ በወታደራዊ ኮሎኔሎች ከህንድ ተገዝቶ የተተከለዉ የአፊምቦል ስኩዋር ፋብሪካና ሸንኮራ አገዳ እርሻና ፡ የቲማቲሙ ማሸጊያ ፋብሪካ፡የሀይኮታ ሙዝና ቲማቲም ማሸጊያ ፋብሪካ የምፅዋ ባህር ልማት ፕሮጀክት፡ ከድባርዋ እስከ አዲኩዋላ የሚገኘዉን የጤፍ እርሻ መሬት ከግል አርሶአደሮች ወርሰዉ በወታደሮች ትራክተር ያሳረሱት እርሻ፡ ለቢራ ፈብሪካ ብቅል ታስቦ ከአስመራ ዙሪያ አርሶአደሮች ተነጥቆ የታረሰዉ የገብስ ምርት ዘመቻ ተዘርዝረዉ የማያልቁት በአረቄ መራሽነት የተነደፉት የባነኮኒ ላይ የቁም ፕሮጀክቶቻቸዉ የመሳሰሉት በሲአይኤና አሜሪካ ሴራ መክነዉ ባክነዉ ስለቀሩ አሁን ግን እዚያዉ በሙሉ ጊዜ ቆመዉ ማሰራት መርጠዋል አሉ፡፡ ምን ያድርጉ የረባ ባለሙያ የለማ! ማንን ሊመሩ ፕሬዚዳንት ይሆናሉ; ሰዉ ሁሉ ወጣ፡፡ በህግደፍ እየተገፉ ከገበያ የወጡትን የግል ኢንቨስትመንቶችና ባለሀብቶችንማ ቤቱ ይቁጠራቸዉ ፡፡ በተለያዩ አፍሪካ አገራት ስኬታማነታቸዉ ይመስክር፡፡ ወጣቱ አዛዉንቱ የቀድሞ ታጋይ ሴቱ ህፃናቱ ከሁዋላዉ በጥይት እያስደበደቡትም መዉጣቱን ቀጥሉዋል፡፡ በዘመነ ደርግ ከነበረዉ ኤርትራዊ ስደተኛ በላይ በድርብ ድርብርብ እጥፍ በበረሀና ባህር እየፈለሰ እየሰነጠቀ የአሳ እራት እሆነ ነዉ፡፡የህግደፍን ዘመነ ርግማን ሽሽት፡፡ እሳቸዉ ግን የተረገመች አሜሪካ ሰዉን አጋዘችዉ ይላሉ፡፡ እናም በቃ ሙያ መቀየር ፈለጉ ማለት ነዉ፡፡ ሰንበትበት ብለዉም የፓትሪርክ ካባ ደርበዉ ብቅ ይላሉ፡፡ ምን ጣጣ አለዉ! አንድ ለናቱ እሳቸዉ ብቻ ናቸዉ ያሉት፡፡ ለነገሩ በፅህፈት ቤታቸዉ ዉስጥና ዙሪያ የሚዘዋወረዉ የዕልፍ አዕላፍ ንፁሀን ህይወትና ጣዕረ ሞት ስለሚያባንናቸዉ ደጅ ደጁን ቢሉ አይገርምም፡፡
ኢሳያስ የዚያን ወራት ከከተማ ወጥተዉ የከተሙበት ጉዳይ ነገሩ ወዲህ ነበር አሉ፡፡ ከዉስጥ እንደሰማሁት፡፡ እንደተለመደዉ ከዉጭ ሀይሎች ደጎማ ተጥሎላቸዉ የዉጭ ታጣቂዎችን እያሰተናገዱ ነበር አሉ፡፡ ለእኛ አዲስ አይደለም፡፡ በኤርትራ ቆላማ በረሀዎች በርከት ያሉ ፀጉረ ልዉጦች እየገቡ ሲርመሰመሱና ታጥቀዉ ሲወጡ እናዉቃለን፡፡ አሻ ጎልጎል በሚገኘዉ የመንግስት ጋራዥ ዉስጥ አናትና ወለላቸዉ ላይ ለተተኩዋሽ መሳሪያዎች በሚመች መልኩ ተቆርጠዉና ተቀጥለዉ ባህርተሸግረዉ የተጉዋጉዋዙት ቶዮታዎች የት እንደዘመቱ ! ዝርዝሩ ይቆየን፡፡ እናም በግድብ ስራ ስም ሰዉየዉ ሌላ ጉዳይ ይገድቡ ነበር ነዉ የተባለዉ፡፡ የዚያን ሰሞኑ ያልታሰበ የሳዑዲ ጉዞአቸዉ ስለዚሁ ጉዳይ ለመናዘዝ አይሆንም ትላላችሁ? መቼም ሳዑዲአረቢያ ኤርትራን በአይነቁራኛ እንደምትጠብቅ አይጠፋንም!
…………
የአያሌ ፀያፍ ታሪክ ባለቤትና (ሚኒሰትሮቻቸዉን በየቢሮአቸዉና ስብሰባ ላይ መሳደብና ማንቁዋሸሽ፡ ከበረሀ ጀምረዉ ይዘዉት የመጡትን በሀላፊዎች መካከል ሀሜት መንዛትና በበታቾች ፊት የማዋረድ ልምድ(አሁን በእስር ላይ የሚገኙት የትግል አጋሮቻቸዉ በመጨረሻ ሰዓት ከደራሲ ዳን ኮኔል ጋር ባካሄዱት ቃለመጥይቅ እንደተነተኑት) ፡ የሰዉ ሚስት ማማገጥ፡ ከዳንኪራ ቤቶች አይናቸዉ ያረፈባትን ልጃገረድ መንጠቅ፡(መስካሪ የማያሻዉ ባህሪያቸዉ) ሲዞሩ ካመሹበት መሸታቤት በስካር መንፈስ እየጋለቡ ሄደዉ በግፍ ያሰሩዋቸዉ የትግል አጋሮቻቸዉ ላይ መትፋትና መሳደብ፡(እማኝ የእስረኞች ጠባቂ) በተለያዩ ሙያ ጎላ ብለዉ የሚወጡ ዜጎችን ማሳፈን ማስገደል.. አርቲስት አብርሃም አፈወርቂ፡ የኦሞ ፋብሪካ ባለቤት መሀመድ፡ ፍቅረና ሌሎችንም ባለሀብቶች..ነባር ታጋዮች) እንዲሁም የማይጨበጥ ስብዕና ስላላቸዉ እኚህ ሰዉ ጉድ ተዘርዝሮ አያልቅምና ዉስጥ አዋቂዎች ይቀጥሉበት፡፡

እኛ እኚህን የኤርትራና ኢትዮጵያ ህዝቦች አይበጄ ሰዉ ከቶዉኑ ዳግም ላይሸነግሉን ‹ይአክል!› ‹በቃ› ብለናል፡፡ ለባለተራዎችና ‹ የእባቡን ተናዳፊነት ለማረጋገጥ መነደፍን › ለመረጡ ዉርድ ከራሴ! በነገራችን ላይ ‹የአማዉቱና › አባወራ የሆኑት ኢሳያስ ወያኔን ለመገልበጥና ስልጣን ለመቆናጠጥ እስከረዱን ድረስ ስለ ግፉአኑ የኤርትራ ህዝብ ጆሮዳባ ልበስ ማለትና ከኢሳያስ ጎራ መጨፈር በኤርትራ ህዝብ ዋጋ መቆመር በስቃዩ ላይ መረማመድ አይሆንምን? ወገናችን የሚሉት የኤርትራ ህዝብ እንደሚታዘባቸዉ ዘነጉት ይሆን? ታሪካዊና ዘላቂ ወገናዊነቱን መክሰርስ አይደለምን; ህዝብንጂ ነዋሪ መንግስታት ተለዋዋጭ ናቸዉና ዛሬ ከኢሳያስ ጋር የሚወዳጁ ኢትዮጵያዉያን ሀይሎችን የኤርትራ ህዝብ የስልጣን ባለቤትነቱን ሲያረጋግጥ እንደምን ደፍረዉ ያዩት ይሆን? ብዙ ብዙ የትዝብት ህፀፆችን ታሪካዊ የሚባሉ እንከኖችን መምዘዝ የሚቻል ይመስለኛል፡፡ ለመሆኑ ለሳደጋቸዉ የኤርትራህዝብና ለትግል አጋሮቻቸዉ ከሀዲና የግፍ ባለሙዋል የሆኑት ኢሳያስ ለኢትዮጵያና ህዝቡዋ እንደምን መልዐክ ይሆናሉ ተብሎ ይጠበቃል? የኤርትራና ኢትዮጵያ ህዝቦችን መፃዒ ሰላማዊና የፍቅር ግንኙነት የምትተነብዩ አርቆ አሳቢ ወገኖች ስለሁለቱም ህዝቦች የሚበጀዉን በሉ፡፡ ኢሳያስ ግን አሁን አንዳንድ ኢትዮጵያዉያን ተቃዋሚዎችን በአፍም በእጅም እየሸነገሉ ያሉበት ኩነት በዙሪያቸዉ አከማችተዉ ለአማዉቱና ታሪካቸዉ አያዘጋጁ መሆኑን ኤርትራዉያን ይገነዘባሉ፡፡ ምክንያቱም ከንግዲህ ከየትም ይምጣ በኢሳያስ ላይ አንዳች ዉርጅብኝ ከተሰነዘረ እንደ ባድመዉ በሉዓላዊነት ስም ቆሞ የሚዋጋላቸዉ ኤርትራዊ እንደሌለ አሳምረዉ ያዉቃሉና፡፡

እንደትዝብቴ የኤርትራ ህዝብ ኤርትራ ዉስጥ ገብተዉ በሚንቀሳቀሱ ኢትዮጵያዉያን ላይ ቅሬታ የለበትም ፡፡ ጣቱን የሚቀስረዉ የኢሳያስን አስከፊ አገዛዝ ና ዕድሜ ለማራዘም ከህግደፍ ጎን በሚወግኑና ጠባቂዉ ሹምባሽ (ጣልያን ለባንዳዎች ይሰጥ የነበረዉ ማዕረግ ) በሚሆኑት ላይ ነዉ፡፡ ይህ ታሪካዊ ስህተት ይመስለኛል፡፡በሁለቱም ወገን የሚንቀሳቀሱ ተቃዋሚ ወገኖች የሁለቱን ህዝቦች ዘላቂ ዝምድና በሚያበላሹ ይህን መሰል ጊዚያዊ የጭፍን እርምጃዎችን ሊገቱ ይገባል፡፡ስለ ኢሳያስና ስርዓታቸዉ መመስከራቸዉንም ሀፍረት ጣል ቢያደርጉበት መልካም ይሆናል፡፡ከባለቤቱ ወዲያ አዋቂ…ወይንም ‹ብዘመነ ግርምቢጥ ማይ ንዓቀብ !ያስብላልና፡፡ እናም የኢሳያስን ጉዳይ ለግፉዓኑ ተዉ ወይንም ከተገፉት ጎን ቁሙ፡፡ ‹የሱን ለሱ የጲላጦስን ለጲላጦስ› እንዲሉ! ብሎም ከኢሳያስ ጋር ሆነዉ የኤርትራን ህዝብ ወገናዊነትና ልብ እናገኛለን ብለዉ የሚያስቡ ወገኖች ቆም ብለዉ ቢያስቡ መልካም ይሆናል፡፡ ምክክራቸዉም ከህግደፍና ተላላኪዎቹ ጋር ሳይሆን ከአብዛኛዉ የኤርትራ ህዝብ ጋር መሆን ይኖርበታል፡፡ የኢሳያስ ህግደፍ ከኤርትራ ህዝብ የኢምንቶች ከባቢያዊ ቡድን ስብስብ ስለመሆኑ አከራካሪ ባለመሆኑ ይህንኑ አበክረዉ ሊገነዘቡ ይገባል፡፡ ኢሳያስ የኢትዮጵያ ህዝብ ብቻ ሳይሆን የኤርትራ ህዝብም ጠላት እንጂ ወዳጅ ከቶዉንም ስላለመሆኑ አሁን እንዳዲስ መደናቆር የሚያሻን ወቅት አይደለንምና፡፡
ለኤርትራና ኢትጵያ ህዝቦች እዉነተኛና ዘላለማዊ ፍቅር በርትተን እንቁም!
ሰላም እንሰንብት! ከአዉስትራሊያ፣ ሜልበርን

The post “አማዉቱና!” አሙዋሙቱን (አብረን እንሙት) ሠናይ ገብረመድህን ዮሀንስ (ጋዜጠኛ) appeared first on Zehabesha Amharic.

Sport: ዮሱፍ ሳህላ በአዲሱ አሰልጣኝ በብሄራዊ ቡድን ተጫዋችነት አልተካተተም

$
0
0

Yosuf salah
“የዮሱፍ ሳህላ ወቅታዊ አቌሙን አላውቅም ፤ወቅታዊ አቋሙ የማናቀውን ተጨዋች አንመርጥም” አሰልጣኝ ዮሀንስ ሳህሌ

ኢትዮ ኪክ እንደዘገበው ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ሰሞኑን ከሚታወቁት የመጨረሻዎቹ 23ት ተጨዋቾች በተጨማሪ በውጪ የሚገኙ 5 ተጨዋቾች በአሰልጣኝ ዮሀንስ ምርጫ ተካተዋል።

ከግብፁ ፔትሮጀት ፣ አል ሃህሊ እና ኢቲሃድ ሽመልስ በቀለ ፣ ሳልሀዲን ሰኢድ እና ኡመድ ኡክሪ፣ ከቱርኩ ጊንኪልቢርጊን ዋሊድ አታ፣ ከደቡብ አፍሪካው ቢድቭስት ዊትስ ጌታነህ ከበደ ቡድኑን ይቀላቀላሉ።

ከሶስት ወራት በፊት በውሰት የስዊዲኖቹን ክለብ IK sirius ለቆ AFC united የተባለውን ክለብ የተቀላቀለው ዮሱፍ ሳላህ በአዲሱ አሰልጣኝ ምርጫ ውስጥ አልተካተተም። አሰልጣኝ ዮሀንስ ሳህሌ በትላንቱ መግለጫቸው ስለ ዮሱፍ ሲናገሩ ” ዮሱፍ ሳላህን ወቅታዊ አቌሙን አላውቅም ወቅታዊ አቌሙን የማናቀውን ተጨዋች ደግሞ አንመርጥም እሱን የሚተኩ በርካታ ተጨዋቾች አሉን ” ብለዋል። ዮሱፍ ሳላህ ለክለቡ በሶስት ጨዋታ አንድ ጎል አስቆጥሯል። የሚጫወትበት ኤፍ ሲ ዮናይትድ ክለብ በስዊድን የወንዶች የክለቦች ውድድር ከዋናው ዲቪዚዮን ቀጥሎ 16 ክለቦች ከፍተኛ ፉክክር በሚደረግበት በከፍተኛ ዲቪዙዮን ውስጥ የሚገኝ ነው።

The post Sport: ዮሱፍ ሳህላ በአዲሱ አሰልጣኝ በብሄራዊ ቡድን ተጫዋችነት አልተካተተም appeared first on Zehabesha Amharic.

Health: የራስ ምታትዎን በተመለከተ ሃኪምን ማማከር የሚገባዎ መቼ ነው?

$
0
0

Migrin
(በዶ/ር ሆነሊያት ኤፍሬም ቱፈር)

የራስ ምታት በአብዛኞቻችን ላይ የሚከሰትና እረፍት በማድረግ ወይንም ህመም ማስታገሻን በመውሰድ ወደ ቀደሞ ጤንነታችን መመለስ እንችላለን። ነገር ግን አልፎ አልፎ የራስ ምታት ህመም የሌላ ከባድ የሚባል ህመም መገለጫ ሊሆን ስለሚችል ወደ ሀኪም መሄድ እና ምርመራ ማድረግ ያስፈልጋል።

እነዚህም ሁኔታዎች

✔ ለመጀመሪያ ጊዜ የራስ ምታት ተሰምትዎት የእለት ተዕለት ስራዎ ላይ ተጽእኖ ካስከተለ
✔ ድንገተኛ እና ከባድ የሆነ የራስ ምታት ከተሰማዎ
✔ ከሌላው ጊዜ በተለየ ሁኔታ የራስ ምታት ከተሰማዎ
✔ ከራስ ምታቱ ጋር ተያይዞ ለመናገር መቸገር፣ ለማየት መቸገር እና የእጅና እግር የእግር አለመታዘዝ ካለዎት
✔ በ24 ሰአት ውስጥ እየባሰ የመጣ የራስ ምታት ካለዎት
✔ ትኩሳት፣ የአንገት ህመም ማቅለሽለሽ እና ማስመለስ ከራስ ምታቱ ጋር ከመጡ
✔ የራስ ምታቱ የመጣው ራስዎ ላይ በደረሰ የመመታት ወይንም የመጋጨት አደጋ ምክንያት ከሆነ
✔ ግማሽ ራስዎን ከፍሎ የሚያምዎ ከሆነ እና ከራስ ምታቱ ጋር የአይን መቅላት ወይንም ህመም ካለዎት
✔ ከ50 አመት እድሜ በላይ ከሆኑ እና የራስ ምታት ህመም የጀመርዎ ከሆነ
✔ከዚህ ቀደም በካንሰር ህመም የተጠቁ ከሆነ እና አዲስ የራስ ምታት ከተሰማዎ ናቸው።

The post Health: የራስ ምታትዎን በተመለከተ ሃኪምን ማማከር የሚገባዎ መቼ ነው? appeared first on Zehabesha Amharic.

አይሲኤስ በወገኖቻችን ላይ የፈጸመውን ጭካኔያዊ ግድያ ለመቃወም ሰልፍ የወጣው ናትናኤል 3 ዓመት ከ 3 ወር ተፈረደበት

$
0
0

ነገረ ኢትዮጵያ እንደዘገበው የኢትዮጵያ መንግስት አይ ኤስ አይ ኤስ ኢትዮጵያውያን ላይ የፈፀመውን የጭካኔ እርምጃ ለመቃወም በጠራው ሰልፍ ላይ ‹‹ሁከትና ብጥብጥ›› ፈጥረሃል በሚል ተይዞ የታሰረው ናትናኤል የዓለም ዘውድ የ3 አመት ከ3 ወር እስራት ተፈረደበት፡፡ ዛሬ 25/2007 ዓ.ም የፌደራል መጀመሪያ ፍርድ ቤት መናገሻ ምድብ ችሎት የቀረበው ወጣት ናትናኤል የዓለም ዘውድ ላይ የቀረበው ክስ ‹‹ሁከትና ብጥብጥ መፍጠር›› የሚል ሲሆን አቃቤ ህግ ‹‹ሁከትና ብጥብጡን የፈጠረው ኢትዮጵያውያን ላይ ግድያ የፈፀመውን አይ ኤስ አይ ኤስ ለማውገዝ የተጠራው ሰልፍ ላይ በመሆኑ፣ በተፈጠረው ረብሻ በርካታ ሰዎች የተጎዱ በመሆኑ እና ረብሻውን የፈፀመው አምስተኛው አገራዊ ምርጫ እየተቃረበ ባለበት ወቅት በመሆኑና ይህም አደጋውን ያባብስ የነበር መሆኑን በማገናዘብ›› የሚል የቅጣት ማክበጃ መጨመሩን ገልጾአል፡፡
nat
በሌላ በኩል በተመሳሳይ ክስ ተከሰው በዚሁ ፍርድ ቤት የቀረቡት ማቲያስ መኩሪያ፣ ብሌን መስፍን፣ ተዋቸው ዳምጤና መሳይ የተባለ ሌላ ወጣት መከላከያ ምስክር ለማቅረብ ለሰኔ 4 ተቀጥረዋል፡፡ እነ ማቲያስ ‹‹ሰልፉ ላይ ሀሰተኛ ወሬ በማውራት፣ ጠቅላይ ሚኒስትሩ እየተናገሩ በነበረበት ወቅት ወደ ፖሊስ ድንጋይ በመወርወር፣ ህዝቡን አትነሳም ወይ በማለት…›› የሚል ክስ የቀረበባቸው ሲሆን በጉዳዩ ላይ ዛሬ ይቀርባል ተብሎ የነበረው የቪዲዮ ማስረጃ ባለመቅረቡ በሚቀጥለው ቀጠሮ እንዲቀርብላቸው ጠይቀዋል፡፡

በተመሳሳይ ‹‹ጠቅላይ ሚኒስትሩ እየተናገሩ በነበረበት ወቅት ወደ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ድንጋይ በመወርወር ሰልፉን አውካችኋል›› የተባሉ ሌሎች አምስት ወጣቶች ለሰኔ 4 የመከላከያ ምስክር እንዲያቀርቡ ተቀጥረዋል፡፡ በሰልፉ ሰበብ ተይዘው የታሰሩት ወጣቶች በቤተሰብ እንዳይጠየቁ መከልከላቸውን ለፍርድ ቤቱ አስረድተዋል፡፡

The post አይሲኤስ በወገኖቻችን ላይ የፈጸመውን ጭካኔያዊ ግድያ ለመቃወም ሰልፍ የወጣው ናትናኤል 3 ዓመት ከ 3 ወር ተፈረደበት appeared first on Zehabesha Amharic.

የኖርዌይና የስደተኞቻችን ፍልሚያ – -በአበራ ለማ

$
0
0

127የዛሬ አራት ዓመት በኖርዌይ ተቀስቅሶ የነበረው የ500 ጥገኝነት ጠያቂ ኢትዮጵያውያን ስደተኖች ጉዳይ በኦስሎ አንደኛ ደረጃ ፍርድ ቤት 127ኛ ችሎት በቅርቡ ሲታይ ሰንብቷል፡፡ ይህ ቀደም ሲል በዶ/ር ግሩም ዘለቀ የግል ተነሳሽነት በኖርዌይ ጠበቆች አማካኝነት በየደረጃው ላሉ የኖርዌይ ፍርድ ቤቶችና በኋላም ለአውሮፓ የሰብዓዊ መብት ጥበቃ ፍርድ ቤት ቀርቦ የነበረው ጉዳይ አሁን የታየው እ.አ.አ. ከሜይ 4 – 29 ቀን 2015 ዓ.ም. ድረስ ነው፡፡ የአውሮፓ የሰብዓዊ መብት ጥበቃ ፍርድ ቤት መቀመጫውን ለንደን ባደረገው ”ዘ አየር ሴንተር – The AIRE Center” (Advice on Individual Rights in Europe) በተሰኘው መንግሥታዊ ባልሆነው የሕግ ባለሙያዎች ድርጅት አማካኝነት የቀረበለትን ይህን ጉዳይ፣ ከሦስት ዓመታት ተኩል በላይ ለሆነ ጊዜ ሲመለከተው መቆየቱም ይታወሳል፡፡—

[ሙሉውን ለማንበብ እዚህ ይጫኑ]

 

 

The post የኖርዌይና የስደተኞቻችን ፍልሚያ – -በአበራ ለማ appeared first on Zehabesha Amharic.

Viewing all 15006 articles
Browse latest View live