Quantcast
Channel: Ethiopian News | ዘ-ሐበሻ | Latest News Provider | News For All
Viewing all 15006 articles
Browse latest View live

የኦሮሞ ፌዴራሊስት ኮንግረስ አለም አቀፍ ድጋፍ ሰጪ ቡድን የተሰጠ መግለጫ –“በምርጫ ተሸንፎ በስልጣን መቆየት አያዋጣም”

$
0
0

ወያኔ/ኢሕአዴግ በምርጫ ተሸንፎ እያለ አጭበርብሮ በሥልጣን ለመቀጠል በሚያደርገዉ መፍጨርጨር ለሚከተለዉ ማንኛዉም ሕዝባዊ ተቃዉሞ ተጠያቂ ነዉ።
የኦሮሞ ፌዴራሊስት ኮንግረስ አለም አቀፍ ድጋፍ ሰጪ ቡድን
Guji 2
በ 2007 ብሄራዊ ሀገር አቀፍ ምርጫ የተለያዩ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ድርጅቶች ከምርጫው ቅስቀሳ ጊዜ ጀምሮ ያለው ሁኔታ ነፃና ፍትሃዊ አለመሆኑን ባወጡት ሪፖርት አረጋግጠዋል::ወያኔ በምርጫው ቅስቀሳ ሂደት ድብደባ፣ አፈና ፣እስራት ፣ግድያ እና እንግልት በግልጽ ፈጽሟል:: (በምዕራብ ሸዋ ዞን ሚዳቀኝ እና በአርሲ ኮፈሌ የተፈጸመው ግድያ ፤ በእነ በቀለ ገርባ ላይ በበደሌ፣ ጅማ እና በነቀምቴ የተፈጸመውን ድብደባ ልብ ይሏል)::

ተቃዋሚዎች ወያኔ ኢሕአዴግን በምርጫ ክርክር አዋረዷት:: ህዝቡ ለመድረክ የሰጠው ድጋፍ ስላስደነገጠው ሃይልን በመጠቀም ጫና ቢያደርግም አልተሳካላትም:: ተስፋ ስቆርጡ ለምርጫው ሁለት ቀናት ሲቀሩት ጠ/ሚኒስትሩ ፓርላማው በማይጠራበት ወቅት ስብሰባ በመጥራት ማስፈራሪያ እና ዛቻ በተቃዋሚዎች ላይ ሰንዝረዋል:: ይህም አስቀድሞ የምርጫውን ውጤት ለመቀልበስ በሃይል ምርጫውን ለማጭበርበር ቅድመ ዝግጅት እያደረጉ እንደነበር የሚያስይ ነበር :: የኢሕዴግ ካድሬዎች የምርጫው ዋዜማ ሌሊት ከአለቆቻቸው የተላለፈውን ትእዛዝ ለመፈጸም አስቀድመው ኮሮጆ በመሙላት በሁሉም የምርጫ ጣቢያዎች የፌዴራል ፖሊስ: ሚሊሺያዎች: ፈጥኖ ደራሽ ፖሊስ እና አድማ በታኝ ፖሊሶችን በማዝመት የምርጫ ቦርድ ተወካዮችን እና የተቃዋሚ (የመድረክ) የምርጫ ታዛቢዎችን መታወቂያቸውን በመቀማት እያስፈራሩ እየደበደቡ በርካቶችን (90%) ሙሉበሙሉ ማለት ይቻላል ከምርጫ ጣቢያ በሀይል አባረዋል።በርካታ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች የምርጫ ካርድ ተከልክለዋል። የመምረጥ መብታቸዉን ተነፍገዋል።

ስለሆነም: ፀረ ሠላም እና ፀረ ዴሞክራሲ የዘረፋ ቡድን የፈጸመው ምርጫን ማጭበርበር ፣ የህዝብ ድምፅ መዝረፍ፣ ንጹሃን ዜጎችን መግደል እና የማሰር ድርጊት አጥብቀን እያወገዝን የኦሮሞ ፌዴራሊስት ኮንግረስ አለም አቀፍ ድጋፍ ሰጪ ቡድን ይህን መግለጫ አውጥቷል።

1. ኦፌኮ/ መድረክ በኦሮሚያ ክልል ምርጫዉን ሙሉ ለሙሉ አሸንፏል።
2. የተፈፀመው ድርጊት በማንኛውም አለም አቀፍ የምርጫ መስፈርት ተቀባይነት የሌለው እና ህገ ወጥ መሆኑን እንገልጻለን:: በጽኑ እናወግዛለን::
3. ይህንን የህዝብ ድምፅ ዝርፊያ እና የምርጫ ማጭበርበር ተከትሎ ለሚነሳው የህዝብ ተቃውሞም ሆነ መንግሥት ለወሰደው እና ለሚወስደው እርምጃ ተጠያቂው እራሱ ኢሓዴግ ነው።
4. የህዝቦች ህገመንግስታዊ መብቶች በተጣሰበት፣ በማፈንና በማስፈራራት ምርጫ አስፈፃሚዎች እና የምርጫ ታዛቢዎች ተባረው ምርጫ ተካሂዷል ለማለት አንችልም።
5. ህዝባችን የመረጠው ድርጅት ኦ.ፌ.ኮ /መድረክ/ የሚያደርገውን ቀጣይ የትግል ጥሪ ዝግጁ በመሆን እንዲጠብቁ እናሳስባለን ።
6. የወያኔን አፋኝ ስርአት እድሜ ለማሳጠር በትግል ላይ የምትገኙ ሃይሎች: ወያኔ ይህን ያህል ረጅም ዓመታት በስልጣን ላይ ሊቆይ የቻለው በራሱ ድርጅታዊ ጥንካሬ ሳይሆን የተቃዋሚ ሃይሎች ትግሉን በተቀናጀ ሁኔታ ያለመምራት በመሆኑ በቀጣይ ለሚደረገው ትግል የፖለቲካውን ክፍተት በመዝጋት ትግሉን ወደ ቀጣይ ምዕራፍ ለማሸጋገር በመተባበር እና ልዩነቶችን በማጥበብ እንድንታገል ጥሪ እናቀርባለን።

ትግሉ ይቀጥላል !!!!!!!!

የኦሮሞ ፌዴራሊስት ኮንግረስ አለም አቀፍ ድጋፍ ሰጪ ቡድን

The post የኦሮሞ ፌዴራሊስት ኮንግረስ አለም አቀፍ ድጋፍ ሰጪ ቡድን የተሰጠ መግለጫ – “በምርጫ ተሸንፎ በስልጣን መቆየት አያዋጣም” appeared first on Zehabesha Amharic.

↧

↧

Health: ከልክ ያለፈ ላብ (ሃይፐርሃይድሮሲስ) እና መፍትሄው

$
0
0

sweating
(በዶ/ር ሆነሊያት ኤፍሬም ቱፈር)
ከልክ ያለፈ ላብ ከእጅ፣ከእግር፣ከብብት እና ፊት አካባቢ በመመንጨት ሙሉ ሰውነትን በላብ እንዲዘፈቅ ያደርጋል።
በዚህ ችግር የሚጠቁ ሰዎች መጠነኛ የሚባል የእለት ተእለት እንቅስቃሴ ለማድረግ እስኪቸገሩ ድረስ በከባድ ላብ ይዘፈቃሉ። ከዚያም ባለፈ ለማህበራዊ ችግሮችና በሰው ፊት ለመሳቀቅ እና መሸማቀቅ ይዳርጋቸዋል።
✔ መፍትሄዎች
• ሰውነትዎን በየቀኑ መታጠብ
• ሰውነትዎን ከታጠቡ በኃላ በሚገባ ማድረቅ
• እግርዎ አየር እንዲያገኝ ማድረግ ፣ ጥጥነት ወይም ሱፍነት ያለዉ ካልሲ መጠቀም
✔ ሃኪምዎን ማማከር የሚገባዎት መቼ ነዉ
• የላብ መጠኑ እጅግ በዝቶ የእለት ከእለት እንቅስቃሴዎ ላይ ችግር ካስከተለ
• ከበፊቱ በተለየ ሁኔታ የሚያልቦት ከሆነ
• ያለምክንያት ማታ በላብ የሚዘፈቁ ከሆነ ናቸው።
ጤና ይስጥልኝ

What Is Excessive Sweating?
If you just sweat more than other people when it’s hot or you’re exerting yourself, that’s not usually a sign of trouble. Sweating is a normal reaction when your body’s working harder and needs to cool itself down.

“There are natural variations in how people sweat, just as there are variations in other bodily functions,” says Dee Anna Glaser, MD, vice chair of the dermatology department at St. Louis University and president of the International Hyperhidrosis Society. “Some people start sweating more easily than others.”

True excessive sweating goes beyond the normal physical need to sweat. If you have hyperhidrosis, you may sweat heavily for no reason — when it’s not appropriate to the circumstances.

“Let’s say that the temperature is mild, and you’re not anxious, and you don’t have a fever, and you’re just watching a movie with your family,” says Glaser. “If you’re sitting there sweating profusely, that’s not normal.”

Via Webmed

The post Health: ከልክ ያለፈ ላብ (ሃይፐርሃይድሮሲስ) እና መፍትሄው appeared first on Zehabesha Amharic.

↧

Health: በአፍንጫችን ላይ የሚወጡ ጥቋቁር ምልክቶችን ለማስወገድ የሚረዱ 8 ዘዴዎች

$
0
0

afencha
በፋሲካው ታደሰ

በቆዳችን ላይ የሚወጡ ጥቋቁር ምልክቶች በቀላሉ ልናስወግዳቸው እየቻልን ለእይታ የማይስብ ቆዳ ያላብሱናል።

በቆዳ ላይ የሚወጡትን ምልክቶች በቀላሉ ማጥፋት ይቻላል ማለት ግን አንድ የተሳሳተ አካሄድ በቆዳችን ላይ ጠባሳ ጥሎ ሊያልፍ አይችልም ማለት አይደለም።

ስለሆነም የቆዳችንን ጤና መጠበቅ የዘወትር ተግባራችን ሊሆን ይገባል።

በአፍንጫችን አካባቢ ጥቋቁር ምልክቶች ከታዩ ብዙ መጨነቅ አይገባም የሚለው የስታይል ክሬዝ ድረ ገጽ ዘገባ የሚከተሉትን ቢተገብሯቸው ጥሩ ውጤት ያገኛሉ በማለት አስቀምጧቸዋል።

1. የፊት ንጽህናን መጠበቅ

በየቀኑ ከ2 እስከ 3 ጊዜ ፊታችንን መታጠብ የፊት ቆዳን ጤንነት ለመጠበቅና በአፍንጫ ላይ የሚወጡ ጥቋቁር ምልክቶችን ለማጥፋት አይነተኛ ሚና አለው።

ጥቋቁር ምልክቶች የወጡበትን የአፍንጫችን ክፍል የሎሚ ጭማቂ መቀባትም ይመከራል።

2. የትራስ ልብሶችን መቀያየር

3. የጥርስ ሳሙና

የጥርስ ሳሙናን መቀባት ጥቋቁር ምልክቶችን ለማጥፋት እንደሚያግዝ ይነገራል።

የጥርስ ሳሙናውን በተጎዳው ወይም ጥቁር ምልክቶች በወጡበት ክፍል ላይ በመቀባት ለ10 ደቂቃ መቆየትና በቀዝቀዛ ውሃ መታጠብ ከችግሩ ለመገላገል ከፍተኛ እገዛ እንዳለው መረጃው አመላክቷል።

4. ስቲም

በሞቀ ውሃ መታጠብ አልያም ስቲም ውስጥ መግባትም ለችግቱ መፍትሄ ነው ተብሏል።

ከእንፋሎቱ የሚወጣው ሙቀት የቆዳችን ቀዳዳዎች እንዲከፈቱ ስለሚያደርግ በአፍንጫችን ላይ የሚከሰቱ ጥቋቁር ምልክቶችን ለማጥፋት ይረዳል።

5. የውበት መጠበቂያዎችን ከመኝታ በፊት ማስወገድ

አንዳንድ ሴቶች ቀን ላይ ውበታቸውን ለመጠበቅ የተጠቀሟቸውን ሜካፖች ሳያስወግዱ ወይንም ሳይታጠቡ ይተኛሉ።

ይህም ለቆዳ ጤና አደገኛ መሆኑ የሚነገር ሲሆን በአፍንጫ ላይም ጥቁር ምልክቶች እንዲወጡ ያደርጋል።

ማንኛውም የውበት መጠበቂያ ለቆዳችን ተስማሚ መሆኑን ማረጋገጥና ከተጠቀምነው በኋላም ከመኝታ በፊት መታጠብ ለቆዳችን ጤንነት መዘየድ ነው።

6. ማር

ፊታችንን አልያም አፍንጫችን ማር መቀባት ጥቁር ምልክቶችን በማጥፋት ንጹህ ቆዳን ያጎናጽፋል።

በቀን ለሁለት ጊዜ አፍንጫችን አንድ ማንኪያ ማር በስሱ በመቀባት ከአምስት ደቂቃ በኋላ በቀዘቃዛ ውሃ መታጠብ በተወሰኑ ቀናት ውስጥ ከችግሩ ለመውጣት ያግዛል።

7. የእንቁላል ነጩ ክፍል

በርካታ ሰዎች የእንቁላል ነጩን ክፍል በመቀባት የቆዳቸውን ውበት ሲጠብቁ ይስተዋላል።

ጥቁር ምልክቶች የወጡበትን የፊታችንን ክፍል የእንቁላል ነጩን ክፍል በእጣታችን በመቀባት ለ10 ደቂቃ ያህል እንዲደርቅ መጠበቅ፤ ከዚያም በእርጥብ ጨርቅ ማጽዳት።

8. አረንጓዴ ሻይ

አንድ ማንኪያ የአርንጓዴ ሻይ ቅጠል ከውሃ ጋር በመበጥበጥ ፊታችንን መቀባትም ቆሻሻዎችን በማስወገድ የጠራ ቆዳን ያላብሰናል።

ከላይ የጠቀስናቸው ነጥቦች በአፍንጫ ብሎም በፊታችን ላይ የሚታዩ ጥቋቁር ምልክቶች በቀላሉ ለማጥፋት የሚረዱ ሲሆን ችግሩ ባስ ሲልም በህክምና ተቋማት የሚታዘዙ ቅባቶችና መድሃኒቶች ይኖራሉ።

ምንጭ:- http://www.stylecraze.com

The post Health: በአፍንጫችን ላይ የሚወጡ ጥቋቁር ምልክቶችን ለማስወገድ የሚረዱ 8 ዘዴዎች appeared first on Zehabesha Amharic.

↧

ኢህአዴግ በአዲስ አበባ ምርጫ ክልል በ 70 ከመቶ ድምጽ እየመራ መሆኑ ተነገረ

$
0
0

election 2015 ethiopiaየቱርኩ የዜና ወኪል ትናንት ዘግይቶ ይፋ እንዳደረገው ከሆነ በአዲስ አበባ ከሚገኙ 23 ምርጫ ጣቢያዎች ውስጥ በ 16ቱ የድምጽ ቆጠራው ተጠናቆ ይፋ መደረጉን ተናግሯል፡፡ የምርጫ ቦርድ ምንጮቼ ነገሩኝ ያለው መረጃው በዚህ ቆጠራ ሂደትም ገዢው ፓርቲ ኢህአዴግ በአዲስ አበባ ምርጫ ክልል በ 70 ከመቶ እየመራ እንደሚገኝ ነው ይፋ ያደረገው፡፡ በሀገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች ካሉ ምርጫ ጣቢያዎችም እንደሚሰማው ከሆነ ገዢው ፓርቲ ኢህአዲግ በሚቀጥሉት አምስት አመታት ሀገሪቱን መምራቱ የተረጋገጠ ይመስላል ሲል ነው የዜና ምንጩ የተናገረው፡፡

The post ኢህአዴግ በአዲስ አበባ ምርጫ ክልል በ 70 ከመቶ ድምጽ እየመራ መሆኑ ተነገረ appeared first on Zehabesha Amharic.

↧

የአዲስ ድምጽ ሬድዮ አዘጋጅ ጋዜጠኛ አበበ በለው የወያኔ ማህበራዊ ሚዲያ ሰራዊትን አጋለጠ

$
0
0
Abebe Belew

አበበ በለው

በስደት ላይ የሚገኘው ህጋዊው ቅዱስ ሲኖዶስ በባልቲሞር ሜሪላንድ 41ኛው ጉባኤውን በተሳካ ሁኔታ መጠናቀቁን ሲኖዶሱ ያወጣው መገለጫ ይጠቁማል።በዚሁ መገለጫ ላይ ሲኖዶሱ ራሱን አይሲስ ብሎ በሚጠራው ቡድን የተሰዉትን ወጣቶች የኢትዮጵያውያን ሰማዕታት በሊቢያ ምድር መሰየማቸው እንደዚሁም ቤተሰቦቻችው እርዳታ የሚያሰባስብ በሊቀ ጳጳስ የሚመራ ግብረ ኃይል መቋቋሙን ያስረዳል። በተጨማሪም በዚህ የፈተና ወቅት መለያየቱ እንደማይበጅ አስረድቶ ራሳቸውን በገለልተኛነት መድበው የሚንቀሳቀሱ አብያተ ክርስቲያናትን ከህጋዊ ቅዱስ ሲኖዶስ ጋር አብረው እንዲሰሩ ጥሪ ያቀርባል።

ይህ በእንደዚህ እንዳለ ራሱን ለህጋዊ ሲኖዶስ ተቆርቋሪ በማስመሰል ግን ህጋዊውን ሲኖዶስ ላይ ማህበራዊ ሚዲያ መርዝ የሚረጭ ወጣት አሉባልተኛ ከወደ ላስቬጋስ ብቅ ብሏል።በሳውዝ አፍሪካ የወያኔ ኤምባሲ ተላላኪና ጉዳይ አስፈጻሚ የነበረው ጉደኛ ወደ ላስቬጋዝ ብቅ ብሎ ጃኬቱን ገልብጦ የወያኔ ተቋዋሚ የሕጋዊው ቅዱስ ሲኖዶስ ደጋፊ ሆኖ ተገኝቷል። ህጋዊ ሲኖዶስ ደግሞ የሚደግፈው በሲኖዶሱ ጥላ ስር ሆነው በመላው ሰሜን አሜሪካ፣በአውሮፓ፣በአውስትራልያና በአፍሪካ እየተዘዋወሩ የተሰደደው ኢትዮጵያውያንን እንደዚሁም ህጋዊውን ሲኖዶስ በትጋት የሚያገለግሉትን የወንጌል ገበሬዎችን በመሳደብና በማዋረድ እንደዚሁም ህጋዊ ሲኖዶስ ያልወሰነውን ውሳኔ በማንበብ ነው።በተጨማሪም ሕጋዊው ሲኖዶስ የገንዘብ አያያዝን አስመልክቶ ብክነት እንዳለ የሀሰት ወሬዎችን በማሰራጨት ነው። ዓይናችሁን ጨፍኑ እናሞኛችሁ ነው ነገሩ።

ወያኔ በዘመናችን የኛ የምንለው ነገር እንዳይኖረን የቤት ስራውን ጨርሷል። የኛ የምንላቸውን ተቋሟት ሰርጎ በመግባት ከፋፍሏል፣ የኛ የምንለውን ሲኖዶሱንም እየተጋለ ይገኛል፣ የሲኖዶስን ዓይን የሆኑትን የስደተኛውን አባቶች እያሳደደ ይገኛል። በዚህ ወቅት ነው አክቲቪስትና ጋዜጠኛ አበበ በለው መሰረቱን ዋሽንግተን ዲሲ ባደረገው የሬዲዮ አገልግሎት ይህንን ነገር ተከታትሎ ያጋለጠው። የመለስ ትሩፋት ጸሃፊ አቶ ኤርሚያስ እንዳሳሳበን ወያኔ ወጣቶችን በማህበራዊ ሚዲያ ሰራዊት አሰልጥኖ የሃሰት መረጃ በማቅረብ የአንድነት የኢትዮጵያ ሃይሎችን መከፋፈል ዓይነተኛ ምግባራቸው ነው። በመሆኑም የበግ ለምድ ለብሰው የመጡትን የወያኔ ጀሌዎች እንደ አበበ በለው በየማእዘኑ እናጋልጣችው። ለማንኛውም ጋዜጠኛ አበበ በለው ከሁለት የኃይማኖት አባቶች ጋር ያዘጋጀው ፕርግራም እነሆ ተከታተሉት።

The post የአዲስ ድምጽ ሬድዮ አዘጋጅ ጋዜጠኛ አበበ በለው የወያኔ ማህበራዊ ሚዲያ ሰራዊትን አጋለጠ appeared first on Zehabesha Amharic.

↧
↧

የጥረቱ ሂደት ዕድገት፤ # ፬ –አንዱዓለም ተፈራ

$
0
0
ቀን፤     ማክሰኞ፤ ግንቦት ፲፰ ቀን፤ ፳ ፻ ፯ ዓመተ ምህረት ( 5/26/2015 ) 11፡00 ጠዋት፤ ፓሲፊክ የሰዓት አቆጣጠር
eskemecheአንድ ነገር ጥሩ እየተካሄደ ያለው፤ የመሰባሰቡ አስፈላጊነት በየቦታው ዋና መነጋገሪያ ጉዳይ መሆኑ ነው። ከዚህ አንጻር፤
  • የኢሕአፓ ዴሞክራሲያዊ ጊዜያዊ አስተባባሪ ኮሚቴ ሁለት አባላት መድቦ፤ በቅድመ ዝግጅቱ ላይ ለውውይት ለመሳተፍ ወስነው አሳውቀውኛል።
  • የሸንጎ አባላት በሙሉ ልባቸው ተካፋይ እንደሚሆኑ አሳውቀውኛል።
  • የሽግግር መንግሥት አመራር አባላት ፈቃደኛነታቸውን ከማበረታቻ ቃላት ጋር ልከውልኛል።
  • አብረውኝ እንዲያስተባብሩ ከጠየቅኋቸው መካከል አራቱ ፈቃደኛ ሆነዋል። በአንድነት የሕዝባዊ መገናኛ እስክናበጅ ድረስ፤ ይኼንኑ የኔን የኢሜል አድራሻ ለጊዜው ልንጠቀም ተስማምተናል።
በተጨማሪ፤ ይሄ የመሰባሰብ ጉዳይ የማንም ግለሰብ ሆነ ድርጅት የግል ጉዳይ ስላልሆነ፤
  • ካሁን በኋላ ከማንኛውም ግለሰብም ሆነ የድርጅት ተወካይ ጋር እኔም ሆነ ሌሎች አስተባባሪ አባላት የምናደርገው የስልክም ሆነ ማናኛውም ዓይነት የግንኙነት ልውውጥ፤ ሕዝባዊና ታሪካዊ አስፈላጊነትና ተጠያቂነት ስላለበት፤ የሚቀዳ ነው። የግል ዘመቻ አልያዝንም።
  • የኔን ሆነ የሌሎችን አባላት ማንነት፣ የትምህርት ደረጃ፣ የትግል ተመክሮ፣ የማስተባበር ልምድ ማንም ማወቅ የለበትም። እያንዳንዱ ግለሰብም ሆነ የድርጅት ተወካይ፤ ማወቅ ያለበት፤ ልሹ የሚታገልለትን የግልም ሆነ የድርጅት ዓላማና ግብ፤ ጊዜያዊውን የኢትዮጵያ የፖለቲካ ሀቅና የትግል አሰላለፍ፣ አሁን የሚያስፈልገውን ግንዛቤና አጣዳፊ ተግባር ነው። ከዚያ ተነስቶ ነው ማንም ግለሰብ ሆነ ድርጅት፤ ከሌሎች ጋር ሊያደርገው የሚፈልገውን ግንኙነት የሚወስነው። እኛ እንደ አበረታታች እንጂ እንደእንቅፋት መታየት የለብንም።
  • አሁንም ብዙ ግለሰቦች ለኔ ኢሜል እየላካችሁልኝ ነው። አመሰግናለሁ። በያላችሁበትም በመሰባሰብም ሆነ በግል ይሔኑ የመሰባሰብ ጉዳይ ልታራምዱ ይገባል። ሰዓቱ አሁን ነው። መበርታት አሁን ነው።
  • ከግንቦት ሰባት በድርጅት የተሠጠኝ መልስ የለም።
  • ለኢሕአፓ አመራር፤ ተሳታፊ እንዲመድቡ፤ እስካሁን በነበረው ግንኙነት በኩል፤ ጥሪ በዛሬው ቀን እንልካለን።
አሁን፤ የመጀመሪያውን የመግባቢያ ስብሰባ ማድረጊያ ሰዓቱ ነው። መጀመር የግድ ያለበት ጉዳይ፤ “ይጀመራል!” እየተባለ ውሎ ማደር የለበትም። መጀመር አለበት። የምንጀምረው በሚከተሉት ሰዎች ነው። ቀኑ በቅርብ ይወሰናል።
፩ኛ.      አሰባሳቢ ለመሆን ፈቃደኛ የሆኑ አምስት ግለሰቦች፤
፪ኛ.      በግለሰብ ለመገናኘትና ለመሰባሰቡ ፈቃደኛ ሆነ የተገኙ ስድስት አባላት፤
፫ኛ.      ከጊዜያዊው የኢሕአፓ ዴሞክራሲያ አስተባባሪ ኮሚቴ የተወከሉ ሁለት አባላት፤
፬ኛ.      ከሸንጎ አባላት የተወሰኑ ( ቁጥሩ አልተገለጸልኝም )፤
፭ኛ.      ከሽግግር ( ዝርዝሩን ገና አልወሰንም )፤
( ፈቃደኛ ከሆኑ፤ ከማንኛውም ኢትዮጵያዊ የውይይት መድረክም ሆነ የፖለቲካ ስብስብ፤ [EEDN, etc ] ቀርበውና ማንነታቸውን አረጋግጠው ሲገኙ፤ እናስተናግዳለን። )
መመዘኛ ነጥቦቹ፤ ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን የተቀበሉ ናቸው።
፩.  የትግሬዎች ነፃ አውጪ ግንባር የኢትዮጵያ ሕዝብ ዋና ጠላት ነው ብሎ የሚያምንና ለማስወገድ የሚታገል፤
፪.  ኢትዮጵያዊያን በሀገራችን የፖለቲካ ሂደት መሳተፍ ያለብን፤ በግለሰብ ደረጃ በኢትዮጵያዊነታችን ተሰባሰቦ ነው፤
፫.  ይህ ትግል ሀገራዊ ስለሆነ፤ ሁላችንም የተካተትንበት አንድ ኢትዮጵያዊ የትግል ማዕከል ያስፈልጋልና እንፍጠር፤
፬.  የኛ ጥረት፤ የሕዝቡን በሀገር ቤት መነሳሳት ለመርዳትና ከጎኑ ተሰልፎ ለድል እንዲበቃና አስተማማኝ እንዲሆን ነው፤
ESKEMECHE

The post የጥረቱ ሂደት ዕድገት፤ # ፬ – አንዱዓለም ተፈራ appeared first on Zehabesha Amharic.

↧

ይድረስ ለጎንደር ሕዝብ ቁጥር #6 “ባለቤቱን ካልናቁ አጥሩን አይነቀንቁ”

$
0
0

Gondor Hibret

የጎንደር ህብረት ዛሬ ይህንን መግለጫ ለማዉጣት የተገደደዉ የወልቃይት ጠገዴ ህዝብ ወደ ነባር የእናት ጎንደር አስተዳደር ለመመለሥ መብቱን ለማስከበር የጠየቀዉን ጥያቄ የወያኔ መንግስት ጀሮ ዳባ ልበስ ብሎ እስከ አሁን ምላሽ ሳይሰጥ እሥራትና ግድያዉ እየባሰ መምጣቱ እጅግ አሳሳቢ መሆኑን ለዓለም ህዝብ ለማሳወቅ ሲሆን፤ እንዲሁም በሱዳን በኩል መሬት አሳልፎ የመስጠቱ ድብቅ ሤራ እስከ አሁኑ ሰዓት ቀጥሎ የትግራይ ታጣቂ ሚሊሻና የሱዳን ወታደሮችን ተመሳሳይ መለዮ ለብሰዉ በመተባበር በጎንደር ህዝብ ላይ ጦርነት መክፈታቸውን ለመላዉ የኢትዮጵያን ህዝብ ለማስገንዘብ ነዉ።

የሁመራ፤ ወልቃይት ጠገዴ እና የጠለምት ህዝብ ሥብዕናዉን ተገፎ፤ የዘር ማጽዳትና የዘር ማጥፋት ወንጀል ተፈጽሞበት፤ የሞተዉ ሙቶ የተረፈዉ ለስደት ተዳርጎ በባዕድ አገር እየታረደ፤ ሃገራዊ ዉርደት ደርሶብን በቁጭት ሃዘን ላይ አለን። አሁንም በአርማጭሆ፤ በመተማና በቋራ በኩል ከዉጭ ኃይል ጋር ተመሳጥሮ ቀስ በቀስ አራሽ ጎንደሬዉን ማፈናቀሉን አላቆመም። የወገኖቻችን ህይዎት በየቀኑ እየተቀጠፈ፤ ቤት ንብረታቸዉ እየወደመ ነዉ። ከዚህ ሁሉ ግፍ እና በደል የተረፉትን ወንድምና እህቶቻችን ወደባእድ አገር እንዲሄዱ የእርጎ ባህር በማሳዬት፤ በራሱ የደህንነት መስመር የኮንትሮባንድ ንግድ ከፍቶ እያጓጓዘ ገንዘብ የሚቸበችበዉ፤ የሚያሳርደዉ፤ ውቅያኖስ እና በረሃ እንዲበላቸው፤ በሳት እንዲቃጠሉ ምክንያት የሆነው እራሱ አሸባሪዉ ወያኔ ነዉ። — [ሙሉውን ለማንበብ እዚህ ይጫኑ]—- —

 

The post ይድረስ ለጎንደር ሕዝብ ቁጥር #6 “ባለቤቱን ካልናቁ አጥሩን አይነቀንቁ” appeared first on Zehabesha Amharic.

↧

አምስተኛው ዙር የድምጽ ዘረፋ… (ክንፉ አሰፋ)

$
0
0

የ”ምርጫው” ድራማ እየተተወነ ሳለ፤ የቦርዱ ሊቀመንበር ዶ/ር መርጋ በቃና እና ምክትል ሊቀመንበሩ ዶ/ር አዲሱ ገብረእግዚአብሔር ለአቦይ ስብሃት ስልክ ደወሉ።

“ሃሎ?”

“ሃሎ፣ አቦይ ስብሃት ኖት?”

“ነኝ፣ ምን ፈለግክ?”

“ዶ/ር መርጋ በቃና እና ዶ/ር አዲሱ ገብረእግዚአብሔር ነን።”

“ችግር መስማት አልፈልግም። የታዘዛችሁትን አደረጋችሁ?”

“99.8% ህዝብ አልመረጠንም። ግን በታዘዝነው መሰረት ውጤቱን ገልብጠነዋል!”

“0.2% ብቻ ነው የመረጠን ማለት ነው?”

“አዎን ጌታዬ። ሌላ ምን እንታዘዝ?”

“99.8% ህዝብ የስም ዝርዝሩን አንብብልኝ።” አሉ አቦይ ስብሃት እየተባለ ይወራል።

election 2015 addis ababaአንድ ወዳጄ ስለ አቦይ ስብሃት የነገረኝ ታወሰኝ። ሰውዬው ከግመል እንኳን የማይሻል እንስሳ ብጤ ነው። ግመል ሳትጠጣ ለቀናት ትሰራለች አቦይ ስብሃት ደግሞ ሳይሰራ ቀኑን ሙሉ ይጠጣል። አብዛኞቹ የህወሃት አባላት እድሜያቸው እንደ አስተሳሰባቸው ስላረጀ ጨዋታቸው ከውሃ ጋር ነው። ከውድ ውሃ ጋር! ድንጋይን ውሀ ያስጮኸዋል!

ሜዳው የኢህአዴግ፣ ዳኛው ኢህአዴግ፣ ታዛቢው ኢህአዴግ፣ ድምጽ ቆጣሪው ኢህአዴግ እንዲሆን ተደርጎ የተዘጋጀው “ምርጫ” እነሆ ተጠናቀቀ። በአፈና የታጀበው ምርጫ ጸጥ-እረጭ ባለ ድባብ ተጠናቅቋል። ልክ አስገድደው እንደሚደፍሩ ወሮበሎች፤ በሃይል ጠልፈው ያላቻ ትዳር እንደሚመሰርቱ ጉልበተኞች፣ የኢትዮጵያ ሕዝብ ያለፍቃዱ እንደገና የአምስት አመት የትዳር ቁርኝት ውስጥ ገብቷል። ሌላ አምስት አመት። ሌላ የህወሀት ዘመን። ሌላ የጥርነፋ ዘመን! ሌላ የቁምራ ዘመን! ሌላ የመፈናቀል ዘመን! ሌላ የመሬት ነጠቃ ዘመን! ሌላ የስደት ዘመን!…

የህወሃት ሰዎች አሁን የጭንቀቱ ምእራፍ ሁለት ላይ ናቸው። በዛሬው እና በትላንቱ እለት የህወሃት ባለስልጣናት ተሰባስበው በፐርሰንቱ ምደባ ላይ ውይይት ይዘዋል። ዘረፋው ላይ ሁሉም በ 100% ይስማማሉ። ምደባው ላይ ግን ችግር አለ። አንዳንዶቹ ይህ ጉዳይ ተአማኝነት እንዲኖረው ለተቃዋሚዎቹ ትንሽ መልቀቅ ይኖርብናል ሲሉ ለሎች ደግሞ ይህንን ሃሳብ ይቃወማሉ። ጥቂት ተቃዋሚዎችን ፓርላማ እንዲገቡ መፍቀድ አለብን የሚሉ ተከራካሪዎች “ሌባ ከሰረቀው ጥቂቱን ቢሰጥ” እንደማይጎዳው ይናገራሉ። ይህንን የማይቀበሉት ግን የተቃዋሚዎች በፓርላማ መግባት ራስ ምታት እንደሚሆንባቸው በስፋት መክረዋል። 547 መቀመጫ የነበረው የቀድሞው ፓርላማ ውስጥ እውነትን የያዘ አንድ ተቃዋሚ ብቻ ጭንቅላታቸውን በጥብጦት እንደነበር ሁሉም አይዘነጉትም። ይህንን በድጋሚ መፍቀድ አልያም ውግዘቱን በመቀበል መሃል ባለ አጣብቂኝ ውስጥ ከርመዋል። ውጤቱን ከሰሞኑ ይፋ ያደርገዋል ዶ/ር መርጋ።

የዘንድሮው ዝርፍያ ጤናማ አይደለም። ልክ እንደ ቦራት ዘ-ዲክታተር ፊልም ተወዳዳሪዎችን እግር እግራቸውን እየመቱ ለብቻ ሮጦ፤ በራስ ዳኛ የድል ዋንጫ መረከብ? ይህ በእውነት በዚህ በ21ኛው ዘመን እጅግ የሚያሳፍር ተግባር ነው። ተቃዋሚ ሃይሎች በምርጫው ክርክር እና በትውልድ ስፍራቸው ላይ የነበራቸው የሕዝብ ድጋፍ ምን ያህል እንደሆነ በግልጽ በታየበት ሁኔታ ህወሃቶች 100% አሸንፈናል ሲሉ ከሌብነታቸው ይልቅ ንቀታቸው ጥርስ የሚያስነክስ መሆኑን ለአፍታ እንኳ አላስተዋሉትም። እጅግ ትንሽ ጭል ብላ የነበረችውን ዲሞክራሲ በምድረ ኢትዮጵያ ገድለው፣ ከፍነው ቀበሩት። አዲዮስ ዲሞክራሲ…

ፈረንጆች የሚሉት አባባል አለ። “ለነብሰ-ገዳዮች ትክክለኛ ዲሞክራሲ ማለት ፍጹም አንባገነን መሆን ነው።”

“በ100% ድምጽ ተመርጠናል!” አሉ። የመረጣቸው ህዝብ የቱ ይሆን? በአዲስ አበባ በነቂስ ወጥቶ “ወያኔ በቃን! መንግስቱ ይግደለን” ያለው ህዝብ ነው ወይንስ ለም መሬቱን ተነጥቆ ለባእድ የተሰጠበት የገጠር ህዝብ? በጋምቤላ፣ በቤንሻንጉል፣ በሁመራ…ወዘተ የተፈናቀለው ህዝብ ነው የመረጣቸው? ወይንስ አምቦ – ጉደርን እንደ ሱናሚ ያጥለቀለቀው ህዝብ ? የቱ ነው ወያኔን የመረጠው? ከስርአቱ ጋር ሆድና ጀርባ የሆነው ሙስሊሙ እምነት ተከታይ ነው ወይንስ በእምነቱ ጣልቃ እየገቡ ካድሬ ጳጳስ የሚሾሙለት ክርስቲያኑ ህብረተሰብ? ማን ነው ህወሃትን የመረጠው? እንደ ምጽዓት ለስደት እያኮበኮበ ያለው ስራ-አጥ ወጣት ነው ወይንስ በአነስተኛና ጥቃቅን ተደራጅቶ ድንጋይ የሚፈልጠው ወጣት ምሁር? መብራት እና ውሃ በፈረቃ ያደረጉበት ህዝብ ነው የመረጣቸው?… ለመሆኑ ስንት አመት ነው ህዝቡ ላይ እንዲህ የሚቀልዱት?

እነሱ ልባቸው በትእቢት ስለተወጠረ፤ ሌላው ህዝብ የማይመለከትና የማይሰማ ይመስላቸው ይሆናል። ትእቢት ደግሞ የውድቀት ምልክት ናት። በመጀመርያ የውጭ ታዛቢዎች እንዳይገቡ ተደረገ። ዝም! በምርጫው ወቅት ደግሞ የተቃዋሚ ፓርቲ ታዛቢዎችን አሰሯቸው። አሁንም ዝም ተባለ። ከዚያ ኮሮጆ እየተሞላ ቀረበና በቁም ያሰሯቸው ታዛቢዎችን ምሽት ላይ ፈትተው እንዲፈርሙ አዘዝዋቸው። የተያያዙት አስገድዶ መድፈር ነውና አንዳንዱን አስገድደው በተሰረቀ የድምጽ ሳጥን ላይ አስፈረሟቸው። ምርጫ 2007 በዚህ ሁኔታ “ሰላማዊ፣ ፍትሃዊ፤ ዲሞክራሲያዊና የህዝብ ተዓማኒነትን አግኝቶ” ተጠናቅቋል ሲሉ ፕ/ር መርጋ በቃና አበሰሩ። እኚህ ፕሮፌሰር ግን ህሊና ይኖራቸው ይሆን? ካላቸው በምን ለወጡት? በገንዘብ? ህሊና ስንት ያወጣል?

አለም አቀፍ መገናኛ ብዙሃን ከምርጫው በኋላ ስላለው ነገር ብዙም አላሉም። ማን እንደሚያሸንፍ እና በምን ያህል ድምጽ እንደሚያሸንፍ አስቀድመው ዘግበው ስለነበር ውጤቱን መድገም የፈለጉ አይመስልም። አስቀድሞ ውጤቱ የታወቀበት ምርጫ መሆኑን አለም አቀፍ መገናኛ ብዙሃን ብቻ ሳይሆኑ፣ ራሱ የምርጫው ቦርድ በድረ-ገጹ ላይ በግልጽ አስቀምጦት ነበር። የምርጫው ቦርድ በድረ-ገጹ እንዳስቀመጠው የኢሕአዴግ 501 ተወዳዳሪዎች የተመዘገበለት ሲሆን መድረክ 270፣ የሰማያዊ ፓርቲ 139 እጩዎች ብቻ እንዲኖራቸው ተደረገ። የሰማያዊ ፓርቲ 200 እጩዎች በምርጫ ቦርዱ ተሰርዘውበታል። 108 እጩዎች አስመዝግቦ የነበረው አንድነት ፓርቲም ስልታዊ በሆነ ዘዴ በቦርዱ እንዳይሳተፍ ታግዷል። ይህ እንግዲህ በሎተሪ ሰበብ የተገለሉትን ሳይጨምር ነው።

መቼም ይታገሉታል እንጂ አይታደሉትምና ቀኑ እስኪደርስ የኢትዮጵያ ሕዝብ ባልፈለገው ሊገዛ፤ ባላመነበት ሊዳኝ፣ ባልመረጠው ሊተዳደር ነው። አሁንም ዝምታን መርጧል። ዝምታ ራሱን የቻለ መልስ ነው። በዝምታ የተዋጠች እያንዳንድዋ ሰከንድ ቁርሾ ይዛ ማለፍዋም ግልጽ ነው። ማሰብ ላልተሳነው ሁሉ ዝምታ ያስፈራል። ምጥና ውሃ ሙላት በድንገት እንዲሉ ዝም ያለ ወራጅ ሲወስድ አይታወቅም። ጽዋም ሲሞላ ይፈስሳል…

አለም-አቀፉ ህብረተሰብም ዝርፊያውን ስለለመደው ችላ ብሎታል። የእንግሊዙ “ዘ ጋርዲያን” ጋዜጣ “ምርጫውን ለአብዛኛው ኢትዮጵያዊ እንደ አንድ ክስተትም አይቆጥረውም።” ሲል፣ ሂዉማን ራይትስ ዎች፤ አምነስቲ ኢንተርናሽናል፣ ፍሪደም ሃውስ፣ ሲፒጄ፣ የመሳሰሉት አለም አቀፍ የመብት ተከራካሪ ተቋማት አፈና የሰፈነበት እና ነጻ ሜድያ በሌለበት ሁኔታ የሚካሄደው ይህ ምርጫው ፍሱም ኢ-ፍትሃዊ እንደነ ገልጸዋል። አልጃዚራ፣ ዋሽንግተን ፖስት፣ ኒውዮርክ ታይምስ የመሳሰሉ ታላላቅ ሜድያ ውጤቱ አስቀድሞ የታወቀ ምርጫ ሲሉ ሂደቱን በክፉ ኮንነውል።

ነገሩ ግልጽ ነው። ነጻ ሜድያ በሌለበት፣ ገለልተኛ ታዛቢዎች ባልተፈቀዱበት፣ ነጻ ዳኛ በልተመደበበት ነጻ ምርጫ አይታሰብ። የዘንድሮው ክስተት ህወሃት የዘረፋ ደረጃውን ያወረደበት ምርጫ ነው። ከረቀቀ የዘረፋ ስልት ወደ ግልጽ የውንብድና ተግባር።

የጀርመን ድምጽ እንግሊዝኛው ክፍል ከምርጫው በኋላ ምንጮችን ጠቅሶ ሲዘግብ “ታዛቢዎ የቁም እስር ላይ ስለነበሩ ወደ ውጭ ወጥተው ምርጫውን መታዘብ አልቻሉም” ብሏል። የሰራዊት እና የሚሊሽያ አባላት በየምርጫ ጣብያው እየተገኙ መራጮችን እያስፈራሩ የተካሄደ ምርጫ በአለም ላይ ይህ ብቻ ነው። የምርጫ ዘመቻም በታጠቁ ሃይሎች ወታደራዊ ትእይንት የተካሄደው በኢትዮጵያ ብቻ ነው።

30 አመት ሙሉ ያል ህዝብ ፍቃድ በስልጣን መቆየት ይሰለቻል። እነዚህ ሰዎች የምእተ አመቱን አንድ አራተኛ የሃገሪትዋን ሃብት ብቻ ሳይሆን የህዝብን ድምጽም እየዘረፉ ተቀመጡ። ባለፉት 24 አመታት በአሜሪካ አምስት ግዜ መንግስት ተቀይሯል። በሆላንድ 7 ግዜ መንግስት ወርዶ በህዝብ ድምጽ ሲቀየር አይተናል። አፍሪካዊቷ ጋና አምስት ግዜ ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ ፣ ሶስት ግዜ ፓርላሜንታዊ ምርጫ አድርጋለች።… ያልታደልን ወይንም ያልታገልን እኛ ግን ለ30 አመታት በአንድ አንባገነን ተይዘናል።

ህወሃቶች በሩን ሁሉ ዘግተው ህዝቡን ወደማይፈለገው አመጽ እየገፉት ነው። ያልተረዱት ቢኖር አንደኛው በር ሲዘጋ ሌላኛው በር መከፈት መቻሉን ነው። የ90 ሚሊዮን ህዝብን ድምጽ ሰርቀው፣ አንደበቱን ለጉመው ምን ያህል እንደሚዘልቁ የምናየው ይሆናል። መቶ አመት የዘለቀ አንባገነን በታሪክ አልተከሰተም።

ከዚህ ቀደም ባስነበብኳችሁ ቀልድ ጽሁፌን ልቋጭ። አንድ የህንድ ኢንቨስተር አዲስ አበባ ዮሴፍ ቤተ ክርስቲያንን የቀብር ስፍራ አይቶ በሊዝ ሊገዛ ፈለገ። የአዲስ አበባ ባለስልጣናትን ጠርቶ እንዲሸጡለት ጠየቀ። ባለስልጣናቱም መልሰው ሌሎች ቦታዎች ሳያልቁ የቀብር ስፍራ ለግዜው እንደማይሸጡለት ነገሩት። ህንዱ መለሰና መከራቸው። “እኛ አገር ሰው ሲሞት እናቃጥላለን እንጂ አንቀብርም። ለምን ይህን ለም ቦታ ታባክናላችሁ?” አላቸው። ባለስልጣናቱም መለሱ፣ “እኛ አገር ደግሞ ሰውን በቁሙ እንጂ ሲሞት አናቃጥልም!”

 

The post አምስተኛው ዙር የድምጽ ዘረፋ… (ክንፉ አሰፋ) appeared first on Zehabesha Amharic.

↧

ተቃዋሚዎች የህዝብ ድምጽ ተሰርቋል የሚል ታላቅ የተቃውሞ ሰልፍ ሊጠሩ ነው

$
0
0

11180611_976488465717327_5626230407392496810_n
– ምእራባውያን ዲፕሎማቶች ወያኔን እና ተቃዋሚዎችን ለማስማማት ደፋ ቀና እያሉ ነው::
– ወያኔ እና የምርጫ ቦርድ ባለስልጣናት አሸናፊነታቸውን ለማወጅ እየመከሩ ነው::
– አለማቀፍ ሚዲያዎች እፍረት ያሌለበት ምርጫ ብለው የመሰከሩለት ወያኔ ፍርሃት ለቆበታል::
– ምርጫው ጋር በተያያዘ የተገደሉ ዜጎች አራት ደርሰዋል::
– ታዛቢዎችን እና እጮዎችን ጨምሮ በምርጫው ቀን በተደረገ አፈሳ በመላው ሃገሪቱ ከ500 በላይ ዜጎች ታስረዋል::
– የአፍሪቃ ሕብረት የታዛቢዎች ቡድን የድምፅ መስጪያ ኮሮጆዎች ድምፅ ከመሰጠቱ በፊት ባዶ መሆናቸዉን ለማረጋገጥ ቢጠይቁ እንዳልተፈቀደላቸዉ፤ ኮሮጆዎቹ የቅደም ተከተል መለያ ቁጥር እንዳልተሰጣቸዉ እና የሐገር ዉስጥ ታዛቢዎች ተሳትፎ እጅግ ደከማ እንደነበር አስታዉቋል። Minilik Salsawi (ምንሊክ ሳልሳዊ)

The post ተቃዋሚዎች የህዝብ ድምጽ ተሰርቋል የሚል ታላቅ የተቃውሞ ሰልፍ ሊጠሩ ነው appeared first on Zehabesha Amharic.

↧
↧

ሰብዕዊ መብት ተቆርቋሪነት እና ሥነ –ጥበብ ደምና ሥጋ –ከሥርጉተ ሥላሴ

$
0
0

27.05.2015 /ሲዊዘርላንድ – ዙሪክ/

„ጥበብ፡ ፈጽማ፡ የጎላች፡ ናት፡ ሥርዓቷም፡ አይልፍም፡ የሚወዷትም፡ ሰዎች፡ ፈጥነው፡ ያዋታል፡ የሚፈልጓትም፡ ሰዎች፡ ያገኙአታል። ለሚወዷት፡ ሰዎች፡ ትደርስላቸዋለች፡ አስቀድማም፡ ትገለጥላቸዋለች። በደጃፉ፡ ስትጠብቀው፡ ሁልጊዜ፡ እርሱ፡ ያገኛታል፡ ወደርስዋ፡ የሚገሠግሥ፡ ሰው፡ አይደክምም።  እርስዋን፡ ማሰብ፡ የውቀት፡ ፍፃሜ፡ ነውና። ፈጥኖ፡ ስለርሷ፡ የሚተጋ፡ ሰው፡ ያለ፡ ሃዘን፡ ይኖራል።“ / መጸሐፈ ጥበብ ምዕራፍ 6 ቁጥር 12 እስከ 16/

ጤና ይስጥልኝ ውዶቼ! ረብ ያለ የሚመስለው የዕንባ ጎርፍ ምጽዕት ለወያኔ ሃርነት ትግራይ ዘረኛ አስተዳደር ማንፌስቶ የአውሎ ደወሉን እዬደወለ ነው። አብረዉት ያሉት ሳይቀሩ „ቆም ብላችሁ አስተውሉ፤ ሁሉንም ትክክል ነው አትበሉ፤ የሰው ልጆችን መብት አረገጥንም – ህግም አልተላለፍነም አትበሉ፤ ዓለማቀፉ ማህበረስብ እዬመሰከረባችሁ ነው ጭካኔያችሁንም እያጋለጠ ነው። ባለፈው ወርም አንድ የሰማዕታት የሃቅ ዕድምታ በረጋጩ ማንፌስቶ ላይ ያለን ግልጽ የወቀሰ መንፈስ በንባብ በድፍረት ቀርቦ አዳምጫለሁ“። ከእንቅልፍ መንቃት መልካም መሆኑ ብቻ ሳይሆን፤ ተዘሎ የነበረው የሥነ – ጥበብ ቤተኛ ህግጋት ከተረገጠበት ጋጥ ቀና እያለ ነው። ገፍቶ እንዲሄድ ሆነ ብርታት እንዲኖረው የሚያደርገው ደግሞ ዕውነቱ ነው። ለእውነት ቆሞ ማናቸውንም መክፈል የቆራጦች – ቁርጥ ነው። ሥጋ ፈራሽ ህይወትም ሃላፊ – ዕውነት ግን አብሪ።

ከሥርጉተ ሥላሴ 02.023.2014 (ሲዊዘርላንድ - ዙሪክ)

ከሥርጉተ ሥላሴ 02.023.2014 (ሲዊዘርላንድ – ዙሪክ)

ተክሊሎቼ – ወደ ዋናው እርእስ ጉዳዬ ከመሄዴ በፊት በአንድ ወቅት „ጋዜጠኝነት የማሰብ ጥበብ ልቅና ነው“ የሚል ወግ ነገር እዚህ ከቤቴ ከዘሃበሻ አቅርቤ ነበር። የጋዜጠኛ ሳዲቅ አህመድን የምርጫ ዘገባ ሳዳምጥ የዕርሴን ፍቹን ለምን አላገኘውም መሰላችሁ። ስለዚህም ምስጋና ከፍቅር ጋር ልልክለት – ወደድኩኝ። ተባረክ! መውደድ – በአክብሮት። ኑርልን – የልብ ዓይን!

አሁን ወደ ጉዳዬ በዕእምሮዬ ሰሌዳ ላይ በቀነ ቀጠሮ ወደ ሰነበተው ጉዳዬ እንሆ አብረን – በትሁት ቅናዊ መንፈስ።„ሰው“ ማዕከለኛው አጀንዳው የሆነው ሥነ – ጥበብ ከሰው በታች ያሉ ማናቸውም ጉዳዮች ፋይዳው አይደለም። ሥነ – ጥበብ ለሰብዕዊ መብት መከበር ግንባር ቀደሙ ጠበቃ፤ ተሟጋች መሆን የሚኖርበት የተፈጥሮው ደም ይሄው በመሆኑ ብቻ ነው። አንድ ሰው በሥነ – ጥበብ ዘርፍ ከመሠማራቱ በፊት መወሰን አለበት። የሚበልጠው ለሥነ ጥበብ ሥነ – ምግባር ሰማያዊ ህግጋት መገዛት ወይንም ለፖለቲካ አስተሳሰብ ፍቅር ደፋ ቀና ማለት። ወይንም ናላ ለሚያዞር ግለኝነት /ኢጎ/ ማደግደግ። ሦስቱም መብት በመሆናቸው አንድ ሰው በመረጠው መጓዙ የተገባ ነው። ግድፈትም – ውግዘትም – ጫናም ሊኖርበት አይገባም። የነፃነት ሲሶ ወይንም እርቦ የለውም። ኢጎን በሚመለከት እራሷ ዓለም ያልፈታችው የተከደነ አምክንዮ አለበት።

ነገር ግን ሁለንም ቀላቅዬ ወይንም አደባልቄ „ሀ“ንም „ለ“ንም „ሐ“ ንም እንዳይከፋው ካለ ከተከፈለ ወይንም ከተሰነጠቀ ድልድይ ላይ ቆሟል ማለት ነው። ሥነ – ጥበብ ህይወቱ እራስን የመግዛት ጥያቄ ነው። መንፈስን ወጥረው ርግበትን ከሚጋብዙ ተርግብጋቢ ግላዊ ስሜቶች እስርም – መላቀቅ። ሥነ – ጥበብ የቂም በቀል ቤተኛ አይደለም ወይንም የቁርሾ አግባቢ አስተርጓሚም አይደለም።እንዲያውም ቁርሾ ሆነ በቀል የሰው ልጅ ስውር መርዞች ስለሆኑ አጥብቆ ይጠላቸዋል። እንዳይጠጉትም – ይሸሻል። ሥነ ጥበብ ብሩኽ ብርሃን በመሆኑ ወደ ኋላ ተመልሶ ጨላማን አያንቆለባብስም። ጨላማ ስል ያለፈን ንትርክ ማለቴን ነው።

በሥነ ጥበብ ሥነምግባር ውስጥ ውብ በሆኑ፤ ተደማጭነትን ባተረፉ፣ ተከታይ ባገኙ፤ ወይንም ጥቃት ደርሶባቸው በሰቀቀን ላይ ባሉ፤ እስትንፋሳቸው በአረመኔዎች – በአውሬዎች ሥር የወደቁ የሰው ልጆችን ሁሉ ድንበር፤ ቀለም፤ ጎሳ፤ ሙያ፤ ዕምነት፤ ጾታ ሳይለዬው ወይንም ሳይገድበው አብሯቸው ይሰለፋል፤ ስለእነሱ ሲል የላቀውን መስዋዕትነት ደፍሮም – ይቀበላል። በአረመኔዎች በተለይም በአንባገነኖች ሥር የወደቁ የሰው ልጆች ሁሉ ክስ የለባቸውም። ውንጀላ – የለባቸውም። መከራቸው ሰምዕትነትን – ስለሚያሰጣቸው ጻድቅ ናቸው። ከሰው ልጅ እጅ ወድቆ መተንፈሻ ቧንቧ የተዘጋ – መኖሩን የተቀማ እንዴት ይከሰሳል?!

ከዚህ ማዕቀፍ የወጣ የሥነ – ጥበብ ቤተኛ ጋዜጠኛ፤ የራዲዮና የቴሌቪዢን አንባቢ፤ ጸሐፊ፤ ሙዚቀኛ፤ ገጣሚ፤ ባለቅኔ፤ ጸሐፊ፤ ተወዛዋዤ፤ ተዋናይ፤ ተናጋሪ፤ ሰዕሊ፤ ሃያሲ  ወዘተ …. የቅንጣት ታክል የሥነ ጥበብ ቅዱስ መንፈስ እፍታ ያለረፈበት የተገለበጠ ምጣድ ነው። በምጣድ ጀርባ እንጀራ ይጋገራልን?

ዕውነት መሪው ለሆነው የሥነ ጥበብ ሰው ጨካኞች፤ ገዢዎች፤ በዳዮች – የሚወስዱት አሰቃቂ ኢ-ሰብዕዊ፤ ኢ- ፍትሃዊ ኢ- ተፈጥሯዊ እርምጃዎች ሁሉ ሊሰቀጥጡት፣ ሊያስቆጡት፣ ሊያስቆጩት ይገባል እንጂ ደርብና ምድር ወይንም ገበርና እናት ሸማ ሆኖ በሰብዕነት ተፈጥሮ ላይ አብሮ ማደም ወይንም መሰለፍ አይኖርበትም። ወይንም ለክስና ውንጀላ ተባባሪ አይሆንም። ይህ ከሆነ እራሱን ሽጦታል ማለት ነው። እራሱን የሸጠ የሥነ – ጥበብ ሰው ደግሞ መፈጠሩ በራሱ የጲላጦስን ውስጠት ያጎናጽፋዋል – በጠቀራ ይሸበልለዋል።

እንዴት አንድ የጥበብ ሰው፤ ሥነ ጥበብን ከፈጣሪ አምላኩ በጸጋ የተቀበለ – የተቃባ፤ ባለ ልዩ ተሰጥዕዎ የሰው ልጅ ጠላት በሆነው የትግራይ ነፃ አውጪ ማንፌስቶ ሥር የሚጠፉ ዓይኖቹን ለማዬት ይሳነዋል? ሰው እኮ መርፌ አይደለም። መቼ ይሆን በሥነ ጥበብ ዘርፍ የተሰለፉ ወገኖች ተደራጅተው በአደባባይ በይፋ ወጥተው ይህንን ኢ – ተፈጥሮ የሆነውን ማንፌስቶ የሚያወግዙት? ለመቼ ይሆን አባታችን መዳህኒትዓለም ለዬት አድርጎ የቀባላቸውን መክሊተ – ሜሮነ – ህግጋት ረገጣ የሚያውግዙት?  ዕንባ – እሮሮ – ኡኡታን በተደሞና በአርምሞ የእኔ ብለው የሚያዳምጡት ቀኑ መቼ ነው? ከቶስ ለማን ይሆን የሚጽፉት፤ የሚያነቡት፤ የሚሞዝቁት፤ የሚገጥሙት፤ የሚስሉት፤ የሚቀርጹት፤ የሚወዛወዙት፤ የሚተውኑት?! ተፈጥሮስ ቢሆን ዛሬ ወንዞችን – ተራሮችን – አዕዋፋትን እንሳሳትን – ምንጮችን – መሬትን እኩል የማዬት መብት አለን? እነሱም እኮ እስረኛ ናቸው? የቤቱ ጣሪያ ሳይቀር የስጋት መንበር ነው። ታዲያ ጥበብ የት ተነሳታ የት ላይ ትረፍ? እጅግ የማከብረው የሥነ ጹሑፍ መምህሬ አቶ አበበ ኬሪ „ሥነ ጥበብ ከማህበረሱ ጓሮ ይታፈሳል“ ይል ነበር … ማህበረሰቡና ሥነ ጥበብ እስከመቼ በግርዶሽ ይጠቅለሉ? ገላጮችስ መቼ ውስጣቸውን ብቻ ሳይሆን የቆሙበትን መሬት በማስተዋል – ያስተውሉት?!

„ሰው“ ነው እኮ ተዳራሹ ታላቅ ፍጡር፤ ታዲያ እንዲህ ጨለማ ውስጥ ሆኖ፣ ጸጋቸው ተከዝኖ፤ ምርቃታቸው ታሽጎ፤ መቀመጡ ለመቼ ሊሆን – ይሆን? የሥነ ጥበብ ቤተኞች ፍጹም የሆነ አላቸው – አቅም፤ አላቸው – ሃይል፤ አላቸው – አዳማጭ ታዲያ ቀጠሮው ለመቼ ይሆን? ግፍና በደለን ያላጋለጠ ሥነ – ጥበብ፤ ተጋፍቶ አደባባይ ላይ ድምጹን ያለወጣ ሥነ ጥበብ የቃር ስንቅ ነው – ለእኔ። ወይንም በቀበኛ የተባላ አሮጌ ጨርቅ።

ሥነ ጥበብ ለሰብዕዊ መብት ተሟጋች መሆኑ ብቻ ሳይሆን በተፈጠሮው የተሰጠው ሙያ አለው። ህግ። ሚዛኑ እኩል ልኩ።

በነፃነት ትግሉ የተሰለፉትም ቢሆኑ – ጥበብ አድሎ የለባትም፤ ጥበብ ቤንዚን – አታርከፈክፍም፤ ጥበብ ፍቅር ናት። ጥበብ ህይወት – ህያው ናት። ጥበብ ይቀርባይ ምህረት ናት። ጥበብ እስትንፋስ መንፈስ ናት። እንዴት ብርሃን ተከልክሎ እንደ ጥንቸል ሁሉንም መከራ በመቀበል ላይ ላላ ለተዘረፍነው መንፈስ ክስ ይቀርብበታል? አለ የሚባል ክስ እንኳን ቢኖር ቀን መጠበቁ ምን ይሆን የተሳነን? ስለምን ይሆን አሁን ከ10 ዓመት በፊት ለዛውም ካቴናን ባርዱን ላስተናገደ ዘመን – አጥፊ ተዋናይ የምንሻለት?!  — ያለባራው ያ … ዱላ፤ ያ …. ጩኸት ያ … የስቃይ – የድረሱልኝ ድምጽ የእያንዳንዱ ድቀት ጅራፍ ጩኸት ከጥበብ ቤተኛው ጀርባ አላረፈ ይሆን? መቆፈር – ለቀባሪዎች ይመች ይሆናል ሥራቸው ስለሆነ ጉሮሯቸውም፤ – ለጥበብ ሰው ግን ግጥሙ አይደለም? ይልቁንም ሃፍረት ይዛቅበታል – ተንበርክኮ። መከራንና ሰውን፤ ግፍና በደልን፤ ወቅትናን ሁኔታን የማያዳምጥ ጥበብ – ምኑን ይሆን የተቃማው?! !

ህም! ልጆች ዛሬን ሳያውቁት ወላጆቻቸውን – ተቀምተዋል፤ ጽንሶች ዛሬን ሳያዩት – ተጨናግፈዋል፤ ቢያንስ ይህ አይጎረብጥም? ጠቅለል ብሎ ከፖለቲከኞች ጋር ተሰልፎ መንገድን ለይቶ መታገል አንድ ነገር ነው። ግን በሥነ – ጥበብ ቤተኝነት ሥም ሲሆን ግን ይመራል? እስረኞቻችን – ሰማዕቶቻችን – አርበኞቻችን ምስላቸውን አቅርበን – እናስተውለው። ቀድሞ ነገር ከነዚህ መከራን ፈቅደው ከተቀበሉት ጋር እኛ ምንድን ነን? ለመሆኑ አብረን ቁጭ ብለን የመወያዬት አቅም ቢኖረን እንኳን እንችለዋለን? እንኳንስ ለወቀሳና – ለነቀሳ? ማንን አቅም እዬሰጠን ይሆን?! አርበኞቻችን እስር ላይ ዓመት እስከ ዓመት ሙሉ ብርሃን ተነፍገው፤ ከቤተሰብ ተነጥለው፤ ከጠያቂ ተሰውረው፤ ስለመኖራቸው በህይወት እንኳን በማናውቅበት ሁኔታ ላይ፤ በሞትና በህይወት መሃከል እያሉ፤ መከራችን የተሸከመ ነፍስ —-  ስንከስ – ስንዘለዘል – ስንተረተር – ስናብጠለጥል ….. ለመሆኑስ የጥበብ ሰውነታችን ከእኛ ጋር ወይንስ የወያኔ ሃርነት ትግራይ ማንፌስቶ አሸከር ሆነናልን? ባነበብኩት ነገር አላዘንኩም። ይልቁንም ሥነ – ጥበብ የተጋረደችበትን ቁራኛ አስተዋልኩበት እንጂ።

በምንስ እንለይ ይሆን የሥነ ጥበብ ሰውነታቻን ከወያኔ ሃርነት ትግራይ ማንፌሰቶ ደጋፊያት ጋራ? „ብዕሩም ብራናውም ሰውን መተርጎም ካልቻለ እውሃ ሲሄድበት የከረመ አለት ሆኗል። ብዕር – ብራና ሆነ  አዬሩ – እስትንፋሱ – ህዋሱ – ሩሁ ሆነ ህልውናውም የሰውን ተፈጥሮ ማመሰጣር ከመቻል ላይ ነው። ከዚህ ውላዊ – ቃልኪዳናዊ የመዳህኒታአለም አባታችን ስጦታ ጋር መተለለፍ ካለ – ጌጥን የማቃጠል ብቻ ሳይሆን፤ አመዱን እንደ ሰው ደም በጥብጦ መጠጣት ነው አሁንም ለእኔ።

ነገም ቢሆን ከነፃነት በኋላ የሚኖረው የሽግግር ሂደት „ሰው“ „ተፈጥሮ“ የሚለውን በቅጡ መተርጎም ችሎ አክብሮቱን በተግባር ማሳዬት ካልተቻለ፤ ለሰው ልጆች መፈጠር ሚስጥራዊ መለኮታዊ ትርጉም ዕውቅና መስጠት ከተሳነን፤ የነፃነት ትግሉና የሚከፈለው መስዋዕትነት ዕሴት አልቦሽ ነው። ቋሳ ለሚመራት – ቂም ለሚያስተዳድራት፤ ለእከሌ ፍርሰት ተጠያቂው እከሌ ነው እዬተባለ ዛሬም ነገም መከራ ለሚመረትባት ባዕት ከሆነ ድካሙ …. ? ? ? መርዶን ደመርን ነው እዬተጋንለት ያለው ማለት ነው።

የዘለዓለም ዕንባ መድረቅ ችሎ ቢያንስ እዬረባው ሰላሙን ሳይቀማ፤ የራህብ አንጀቱን ከአንገት በማታልፍ እራፊ በተቀዳደች ሰኔል ላይ ጉልበቱን ታቅፎ ወገን በነፃነት ካለፍርሃት እንዲያደር መፍቀድ የማይችል የነፃነት መንፈስ ለእኔ በአፍንጫዬ ይውጣ። ዛሬ ሚሊዮኖች በሥርዓቱ ውስጥ መሥራት ግድ ይላቸዋል። በዚህ አያያዝ ነገም እነዚህን ሚሊዮኖችን ተከሳሽ ለማደረግ መሰናዶ ይሀው ከሆነ ይቅር ትግል። ይህ ወልጋዳ እሾሃማ የነፃነት ትግሉ መስመር ሊሆን ከቶውንም አይገባም።

መከራዋ የኢትዮጵያ በምህረትና በፍቅር ካሳ ማግኘት አለበት። መልካምና መልካም ያልሆኑ ነገሮች በአግባቡ ተጠንተው ለቀጣዩ ጊዜ በሚበጅ መልኩ መደራጀት አለበቻው። መንፈስ መታጠብ አለበት። ከቂምና ከበቀል፤ ከክስና ከስሞታ መጽዳት ውስጥ ይኖርበታል። በተጨማሪ ዛሬ ያሉት ነገሮች ሁሉ እያንዳንዱ ክስተት የሀገራችን መዋለ ንዋይ፤ መንፈስ፤ ንብረት ፈሶበታል። ስለሆነም ከታሪክ – ከትውፊት ብክነት መዳን አለበት – ህልማችን ሆነ ራዕያችን  – ከዚህ አዎንታዊ ሃዲድ ጋር መዋህድ ይኖርበታል። ይህ ለጥበብ ሰው ሆነ የሰው ልጆች ነፃነት ሆነ፤ የተፈጥሮ በረከትን ረጋጣን ለማስቆም ለተሰለፈ ሰው መስመሩና መንገዱ ሊሆን ይገባል። ሚዛን ጠባቂነቱ የሚረጋገጠውም በዚህ ነው። ሥነ ጥበብ የወርቅ ሚዛን ነው ህዋሱ።

ፖለቲከኛው በፈለገው መስመር የፓርቲውን ፕሮግራም ማንፌስቶውን ከሚወግን መንፈስ ጋር ቢሰለፍ ባህሪው ነው። የፖለቲካ መስፈርቱ የሚወዳደረው በሥልጣን ዙሪያ ነው። ሰው የሚለው ተፈጥሮ የሚታዬው በአንጻራዊነት ነው። ይህ የእኛ ብቻ አይደለም ዓለም እንደ ህግ የተቀበለቸው ጉዳይ ነው። ሲሪያ ላይ ህንፃ አይደለም እይፈረሰ ያለው – ትውልድና ታሪክ ነው። ዋጋው የጥፋቱ የሚለካው ግን ከጥቅም ጋር ነው። የጥበብ ሰው ሆነ የሰብዕዊ መብት ተሟጋች የሆነ አንድ ሰው ወደ ፖለቲካ ህይወት ሽግግር ሲያደርግ ምን እንደሚመሰል ለናሙና …. ትንሽ ነገር እንሆ —

  1. አንድ ፎቶ ወስደን ባለቀለማሙን ፎቶ ወደ ነጭና ጥቁር አንቀይረው፤
  2. ከዛ የፎቶውን የብርሃን መጠን እዬቀንስን ስንሄድ ምስሉ ምን እዬሆነ እንደሚሄድ ሞክሩትና ክብሮቼ – እዩት።

በሌላ በኩል ከፖለቲካ ህይወት ወደ ሰብዕዊ መብት ተሟጋችነት ወይንም ወደ ጥበብ ፍቅር ሽግግር ከኖረ ግን ያ ብርሃኑና ቀለሙ ቀንሶ ምስሉ ስስ የነበረው፤ የሰውነት ምስሉን ለመለዬት ያስቸግረው የሰው ምስል እዬጎላ እዬጎለበት ይመጣል። ስለዚህም የሚቀድምበት – የሚመራው – ተክሊሉና ዘውዱ የሰው ልጆች ሰብዕዊ መብት አለመዘረፍ ብቻ ሳይሆን፤ ተፈጥሮ የለገሰን እንሰሳት፣ ወንዞች፣ ተራሮች፣ ምንጮች፤ ዕጽዋት፤ ሸለቆዎችና መሬት እራሷ ለእሱ ልዩ ትርጉም – ይሰጡታል። ያደንቀዋል፤ ያከበረዋል፤ ያፈቀርዋል። ክፍተቶች – ነዳላዎች – ቀዳዳዎች ሁሉ በመልካም ነገሮች ተሞልተው የሰው ልጅ መከራ ብቻ ሳይሆን ተፈጥሮ የለገሰን የውበት አድባሮች ሁሉ ሰላማቸውን እንዲያገኙ – ይተጋል። መታወካቸውም – ያመዋል። ውስጡን – ያቃጥለዋል። ጠበቃም ይሆናል። ባይችል – መልካሙን ይመኛል፤ ውብ – ያልማል።

ወቅቶች የተፈጥሮ ሂደቶች ናቸው። ወቅቶች የሚፈጥሯቸው ክንውኖች ግድፈቶች በመልካም እንዲሸፈኑ መጣር የጥበብ ሰው ዋንኛው ፕሮጀክቱ ነው እንጂ ወቅቶችና ሂደቶች የፈጠሯቸውን ክስተቶች አፋፍሞ ተታኮሱ አይልም። ይህን የጥበብ ሰው ካደረገ ቂምን – ከከበከበ፤ ጥላቻን – ካበረታታ፤ ቋሳን – ከሞሸረ – የትውልድ ደመኛ ነው። ስለዚህም ማህበረሰቡ በጥበብ ሰውነቱ ሆነ በሰብዕዊ መብት ተሟጋችነቱ የሰጠውን ልዩ ፍቅርና ክብር፤ ግርማና ሞገስ ሆነ ተቀባይነት መንጠቅ አለበት። ጊዜም የቅንጣት ማቃጠል የለበትም። በመከረኞች – በተገፉት – ሰውነት ላይ ጅራፉ ሲያርፍ ቶርች ሲሆኑ፤ ሲደፈሩ የጥበብን ሰው ገላም አብሮ መላጡን – መጋጋጡን – በመንፈሱ መረመጡን መቀበል ላልቻለ የጥበብ ሰው የችሎቱ ብይን የሰጡትን አድማጭነት መንጠቅ ነው።

መቋጫ – ንጹህ አዬር ላይ ያሉ ፖለቲከኞችን ሆነ መስመራቸውን መተቸት ያስተምራል፤ ግደፈትን – ያርማል፤ እሩቅ እንዲያስቡ – ያግዛል፤ አቋምንም – ያስተካክላል። ነገር ግን መከራ ላይ ያሉ ወገኖች፤ እስር ቤት ያሉ ሥጋና ደሞችን፤ እዬተጋፋ በሥማቸው ላይ ሚጥሚጣ የሚነሰንስ ወይንም በአጋፋሪነት ከጨካኞች ጋር የተሰለፈ መንፈስ ከሰማይ የተሰጠን ጸጋና ህግጋት ተላልፏልና ውሉ የተደማጭነትን ካባ በመግፈፍ ማወራረድ ይገባል እላለሁ እኔው ሥርጉተ – ሥላሴ። ከመከራ ከእስር በሰው እጅ ቁጥጥር ሥር ከመወል በላይ ሰምዕትነት የለም“  መሸቢያ ሰሞናት – የኔዎቹ።

„የጥበብን፡ አገሯን፡ ማን፡ አገኘው፡ ምሥጢሮቿን፡ ማን፡ መረመረው።“ /መጸሐፈ ባሮክ ምዕረፍ 3 ቁጥር 14/

 

አርበኞቻችን መንገዶቻችን ናቸው – ለእኛ!

የሰማዕታቱ ረድኤት አይለዬን – ለእኛ። አሜን!

ለእኔስ ሰው መሆኔ ብቻ ይበቃኛል – ለእኔ!

እግዚአብሄር ይስጥልኝ።

The post ሰብዕዊ መብት ተቆርቋሪነት እና ሥነ – ጥበብ ደምና ሥጋ – ከሥርጉተ ሥላሴ appeared first on Zehabesha Amharic.

↧

ፊታችንን ከምርጫ ፓለቲካ ወደ ሁለገብ ትግል እናዙር!- የአርበኞች ግንቦት 7 መግለጫ

$
0
0
ግንቦት 18 2007 ዓ.ም
ginbot 7ምርጫ 2007 ተጠናቆ ተወዳዳሪም አወዳዳሪም የሆነው ህወሓት ይፋ ውጤት እስኪገልጽ እየተጠበቀ ነው። ሁሉ በእጁ ነውና ባለሥልጣኖቹ ምን ዓይነት ውጤት እንደሚስማማቸው እስከሚነግሩን ጥቂት ቀናት ይወስዱ ይሆናል። ከፈለጉ ሁሉን የፓርላማ ወንበሮች ሊወስዷቸው ይችላሉ፤ ካሻቸው ደግሞ ጥቂቱን ለተቃዋሚዎች ሊሰጡ ይችላሉ። ወሳኞቹ እነሱ ናቸው። በዚህ የፓርላማ ወንበሮች እደላ የኢትዮጵያ ሕዝብ ድምጽ አንዳችንም ሚና የለውም።
ምርጫ የሕዝብ የሥልጣን ባላቤትነት ማረጋገጫ ከሆኑ አቢይ ዲሞክራሲያዊ ተቋማት አንዱ መሆኑ የታወቀ ነው። ሆኖም ግን ነፃ ተቋማት በሌሉበት፤ በአምባገነኖች አስፈፃሚነት የሚደረግ ምርጫ የመራጮች ነፃ ፍላጎት መግለጫ በመሆን ፋንታ የገዢዎች ሥልጣን ማረጋገጫ መሣሪያ ይሆናል፤ ከአገራችን እየሆነ ያለውም ይህ ነው።
የዘንድሮው ምርጫ 2007 ከዚህ በፊት ከነበሩ በባሰ ለአፈና የተጋለጠ የነበረ መሆኑ ከጅምሩ በግልጽ የታየ ጉዳይ ነበር። በአንድነትና በመኢአድ ፓርቲዎች ላይ አገዛዙ የወሰደው የግፍ እርምጃ የዚሁ የምርጫ ዘረፋ ስትራቴጂ አካል ነበር። ከዚያ በተጨማሪም መራጮች እውነተኛ ፍላጎታቸውን በነፃነት መግለጽ እንይችሉ ዘርፈ ብዙ ጫናዎች ሲደረግባቸው ቆይቷል። የተወዳዳሪ ፓርቲዎች አባላት እንደተፎካካሪ ሳይሆን እንደጠላት ሲሳደዱ፣ ሲታሰሩ፣ ሲደበደቡና ሲገደሉ ሰንብቷል። በምርጫው ሰሞንና በዕለቱ በተለይ ከተሞች በባዕድ ጦር የተወረሩ መስለው ነበር። ይህ ሁሉ ስነልቦናዊና አካላዊ ተጽዕኖ ታልፎ የተሰጠው ድምጽ ቆጣሪው ራሱ “ተወዳዳሪ ነኝ” ባዩ ህወሓት ነው።
በእንዲህ ዓይነት ምርጫ መሳተፍ ትርፉ “በሕዝብ ድምጽ ተመረጥኩ የማለትን እድል ለአምባገኑ ህወሓት መስጠት ነው”፤ “ለዓለም ዓቀፍ ማኅበረሰብም የተምታታ መልዕክት ማስተላለፍ ነው”፤ ”ለህወሓት ተጨማሪ ገንዘብ ማግኛና የኢትዮጵያን ሕዝብ መከራ ማራዘሚያ ነው“ በሚል በዚህ ምርጫ ላይ ማዕቀብ እንዲደረግ አርበኞች ግንቦት 7 ለኢትዮጵያ ሕዝብ ጥሪ ማድረጉ ይታወቃል። በርካታ ወገኖቻችን የምርጫ ካርድ ቢያወጡም የደረሰባቸውን ጫና ተቋቁመው በምርጫው ባለመሳተፍ ላሳዩት ጽናት አርበኞች ግንቦት 7 አድናቆቱን ይገልፃል።
ህወሓት በስልጣን ላይ እስካለ ድረስ የምርጫ ጉዳይ እና የምርጫ ፓለቲካ ግንቦት 7 ቀን 1997 ዓም የተጠናቀቀ ቢሆንም እንኳን ተጨማሪ ማስረጃ ለሚፈልጉ ግንቦት 16 ቀን 2007 መጥቶላቸዋል። አሁን ከፊታችን የተደቀነው ጥያቄ የሚከተለው ነው – አገራችን ከህወሓት አፈና ነፃ ለማውጣት ያለን አማራጭ መንገድ ምንድነው?
አርበኞች ግንቦት 7: የአንድነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ ህወሓት ከኢትዮጵያዊያን ጫንቃ የሚወርደው ሕዝባዊ እምቢተኝነትና ሕዝባዊ አመጽን ባቀናጀ ሁሉገብ ትግል ነው ብሎ ያምናል። በዚህም መሠረት ለሁለቱም የትግል ዘርፎች ተስማሚ የሆኑ አደረጃጀቶችን አዘጋጅቷል።
ሕዝባዊ እምቢተኝነት፣ ታጋዩ ከመኖርያ ወይም ከሥራ ቦታው ሳይለቅ በህቡዕ የሚከናወን ትግል ነው። ሕዝባዊ አመጽ ደግሞ ከመኖሪያና ሥራ ቦታ ለቆ መንቀሳቀስን ይጠይቃል። ሁለቱም የትግል ዘዴዎች የህወሓትን ህጎች በመቃወም የሚደረጉ ናቸው። ሁለቱም የትግል ዘዴዎች ድርጅት፣ ዲሲሊንና ጽናትን ይጠይቃሉ። ለድላችን ሁለቱም የትግል ዘርፎች እኩል ዋጋ አላቸው። እናም ከዛሬ ጀምሮ እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ እንደዝንባለውና አቅሙ በሚመቸው የትግል ዘርፍ ይሳተፍ። ሕዝባዊ ኃይልን መቀላቀል የቻለ ይቀላቀል፤ ያልቻለው በያለበት ተደራጅቶ በሕዝባዊ እምቢተኝነት ይታገል።
በየመኖሪያ ሠፈሩና በሥራ ቦታዎች የሚቋቋሙ የአርበኞች ግንቦት 7 ማኅበራት በርካታ ሥራዎች አሏቸው። ከሁሉ አስቀድሞ ድርጅትን ማጠናከር የሁላችንም ድርሻ መሆኑ ሊዘነጋ አይገባም፤ እናም ትኩረታችን እዚያ ላይ እናድርግ። እያንዳንዳችን ከሚመስሉንና ከምናምናቸው ጋር ተነጋግረን እንደራጅ፤ ወያኔ የሸረሸረብንን በራስ መተማመን እና የእርስ በርስ መተማመንን መልሰን እንገንባ። ውስጥ ውስጡን ጠንካራ አገራዊ ኅብረት እንፍጠር፤ የዕለት ተዕለት ተግባሮቻችን ደግሞ አካባቢያዊ ይሁኑ። ድርጅታችንን እያጠናከርን ወያኔን ከሁሉም አቅጣጫ እንሸርሽረው እንገዝግዘው። በዚህ መንገድ በሚደረግ ሕዝባዊ ትግል የሚገኝ ድል ፈጣን ከመሆኑን በላይ የድሉ ሕዝባዊነት ጥያቄ ውስጥ የማይገባ ይሆናል።
ስለሆነም እያንዳንዱ ለውጥ ፈላጊ ኢትዮጵያዊ ታጥቆ እንዲነሳ፤ ወደ ተግባራዊ ትግል ፊቱን እንዲያዞር አርበኞች ግንቦት 7 ጥሪ ያቀርባል።
ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!!!
የአርበኞች ግንቦት 7 መግለጫ

The post ፊታችንን ከምርጫ ፓለቲካ ወደ ሁለገብ ትግል እናዙር!- የአርበኞች ግንቦት 7 መግለጫ appeared first on Zehabesha Amharic.

↧

የስፓኙ ፓዴሞስ እና ኢትዮጵያ ህወያት\ኢህአዴግ::ዘጠኝ  ለዜሮ ተለያዩ

$
0
0

ከቢላል አበጋዝ፡ ዋሽግቶን ዲ፡ሲ

በዚህ ሰሞን ሁለት አገራት ህዝባዊ ምርጫ አካሂደዋል።አንዱ የውነት ሌላው የቅጥፈት።የእግር ኳስ ፍቅራችንን እንደያዝነው በምርጫው ሰሞን በስፓኙ  እና ኢትዮጵያ ምን ሆነ? እስቲ እናወዳድር።

TPLF Election signምኞቴ ወደፊት ኢትዮጵያ ስፔኝን ገጥማ መጀመሪያ የህዝብ ምርጫን ጥሩ አድርጋ በመደገስ ቀጥሎ በእግር ኳስ ስታቸንፍ ማየት ነው። የግር ኳስ የምትወዱ ምኞቴን ተጋሩ። በግር ኳስ ከመዝናናት የበለጠ የመቶ ሚሊዮናችንን ህይወት፤የአገራችችን ዕድል ወሳኝ ጉዳይ በዚህ ሰሞን ተካሂድዋል። በስፓኝ ዛሬ ያለው ዲሞክራሲ ብዙ ክፍያ ተከፍሎበታል።በኢትዮጵያም አባት አርበኞቻችን ጣሊያንን እየተዋጉ ሳለ(ሁለተኛ የዓለም ጦርነት)ሪፑብሊክ የመመስረት እልማቸውን አብስረው ስለነበር።ምሳሌ እነ ደጃዝማች ታከለ ወ/ሀዋርያት፡ከዚያ አንስተን ብናሰላው ዘመኑ ረጅም ነው።የኢትዮጵያው እንዲያውም አንድ ትውልድ የወደመበት፤የዛሬው ወጣት ተስፋ የቆረጠበት ፡መሪር ዓመታት ያለፉበት።

የጽሁፉ ዓላማ እዲያው ዝም ተብሎ ስፓኝን ከፍ ለማድረግ ሳይሆን በሁለቱ አገሮች የሆነውን ባጭሩ ለማሳየት ነው። በስፓኝ ከሁሉም በላይ በስልጣን ያለው የጠ/ሚኒስትር ማሪያኖ ራሆይ መንግስት ስልጣን ሲይዝ የስፓኝ የኑሮ ውድነትን አሻሽላለሁ በሚል ቃል ገብቶ ኋላ በሙስና መጋለጡ የህዝቡን ሙሉ ድጋፍ አሳጥቶታል።የራሆይ ፓርቲ፡ፖፑላር ፓርቲ የተሰኘው ብዙ መቀመጫዎች ተቀምቷል። የኢትዮጵያ ጠ/ሚኒስትር ሰው አስጠንቷቸው እንዳሉት “ዲሞክራሲ ባህል ነው”። እርግጥ ነው ጊዜ የሚፈጅ እድገት ነው። ቢሆንም የኢትዮጵያ ህዝብ ያሚያሳየውን የፖለቲካ ብስለት ለተመለከተ ይህ ዲሞክራሲ የሚባል ስልጣኔ ለኢትዮጵያ ህዝብ ቶሎ እንደገባው ማየት አይቸግርም።ለምርጫ ሲሰለፍ ስርዓቱ፤እድሉን ሲያገኝ የውይይት ተሳትፎው ከስፓኝ ወይም ከማንም አያንስም።የኢትዮጵያው ጠ/ሚኒስትር ዳዴ እያስኬደው እንዳለ በባለጌ ድፍረት ቢናገርም።በዚህ የተነሳ ዳኛው በህወያት\ኢህአዴግ ላይ ፍጹም ቅጣት ምት በየነዋል።

ስፓኝ እና ኢትዮጵያ  እሩቅ ለሩቅ ቢሆኑም የሁቱም አገሮች ወይም ማንም ህዝብ ለመብቱ ቀናተኛ ነውና ጎን ለጎን ብናያቸው በዚህ ረገድ ስተት አይሆንም። ወያኔ ኢሀዴግ ውጤቴን ዝቅ አረጋችሁ ብሎ ሊኮንን ይችላል።እንደለመደው ሁማን ራይት ዋችንም (የሰው መብት ተከራካሪ ድርጅት)ግራ ቀኙን መክሰሱ የተለመደ ነው። ከአውሮፓ ግጥሚያው ለማየት የሚመጡት ዘንድሮ ገንዘብ ቸገራቸውም ብሎ የሚቀድ ነው።

በኢትዮጵያ ሰሞኑን ያለፈው የምርጫ ወግ ገና ብዙ የሚወጣ ጉድ ይኖረዋል።ስላለፉት ምርጫዎች ውስጥ አዋቂ ባካፈለን ዛሬ እየተደነቅን አይደለም? በዝርዝር ለታሪክ የሚቀርበውን እየጠበቅን የሰሞኑን ምርጫ እንወያይበት። ትምህርት ወስደን እንቀጥል።ቢያንስ ከዚህ በኋላ በሰላም የስልጣን ሽግግር የሚታሰብ ነው ? በውነት ወያኔ ኢህአዴግ ለዚህ ወግ ይደርሳል።ምርጫውን መካፈል ተቃዋሚዎችን ረዳቸው? እንዴት ? እኒህን ጥያቄዎች መጋፈጥ አለብን። የሃይማኖት ድርጅቶች ተከፋፍለው፤የብሄር ድርጅቶች የወያኔ ኢሀዴግ መሳሪያ ሆነው ወጣቱ በአንድ ጎራ ሳይሰለፍ፤በጥርጣሬ ተይዘን ወደፊት መሄድ ይቻላል ?

ወደ ጨዋታው ስንመለስ የተነሱትን ጥያቄዎች  እያሰብን የቀረበውን ግጥሚያን ባጭሩ የሚያቀርብ ሰንጠረዥ እንመልከት።

 

  ስፓኝ ኢትዮጵያ
1 ህዝቡ በጨዋነት በስርዓት መረጠ።ያፈለገው እየተናገረ መረጠ። ዱላ የለም። ነውር ነው። ህዝቡ በጨዋነት በስርዓት መረጠ።ታፍኖ አይናገርም ነበር።ፖሊስ አጋዚ ሚሊሻ አለ።በቆመጥ በዱላ በጥይት።የህወሃት ብልሃት።
2 ምርጫው ፍጹም ሰላማዊ ነበር። ምርጫው  ፍጹም ሰላማዊ አልነበረም::የሞቱ: የታሰሩ:የተደበደቡ አሉ።
3 በሙስና የተዘፈቁ ጉዳቸው ፈላ። የፍርድ ስርዓቱ ነጻ በመሆኑ ጠቅላይ ሚንስትሩ ሳይቀር ተጋለጠ።850 ሺህ ሰው የተቃውሞ ፊርማ አቀረበበት።ስፓኝን ከችግር ማውጫ ዕቅዱ በመስራቱ ክፉ ላያገኘው ይችላል ይባላል። በሙስና የተዘፈቁ ጫፋቸው አልተነካም።ወያኔን የሚነካ ማን አለ ? የት ሊገባ ?
4 ሁለት ነባር ፓርቲዎች ተቀጡ። አዲስ መጤ ወጣት ፓርቲ ጉድ አፈላ ነባር ፓርቲ ህወሃት ኢሃዴግ አልተነካም

የሰማያዊ ፓርቲ ፍዳውን አየ።መድረክ በደሉን እንደወትሮው ገለጸ

5 ምንም ማስፈራሪያ የለም። ነጻ አገር ነው። ጸረ ሽብር ህግ ማፈኛ፤ማስፈራሪያ
6 ሁሉም ዜጎች እኩል ናቸው ሁሉም ዜጎች እኩል ናቸው  ህወሃት ኢሃዴግ አባላት ከሌላው ከፍ ይላሉ።
7 ወጣቱ የመሳተፍ እድሉ ከፍ ያለ ነበር ወጣቱ ታፍኗል
8 የስፓኝ ቲቪ ጣቢያዎች እንደ ኢቲቪ ውሸታም ሰላልሆኑ ስፓኞች ያገራቸውን ሁኔታ ለማወቅ ሌላ ሚዲያ አያስፈልጋቸውም። ሆኖም በቪኦኤ፤በአልጀዚራ በቢቢሲ ተዘገበ።ከፈለጉ ማዳመጥ መብታቸው ነው። ኢትዮጵያውያን ምርጫውን በኢሳት፡በቪኦኤ፤በአልጀዚራ በቢቢሲ ተከታተሉ።

ኢቲቪ፤ራዲዮ ውሸታም ስለሆነ ለህዝቡ አይጠቅምም።

9 የታሰረ የፖለቲካ እስረኛ የለም። የታሰረ የእንግሊዝ ዜጋም የለም።  ኤታ የተባለውም ተገንጣይ ድርጅት በስምምነት ትጥቅ ፈቷል። ጠ/ሚኒስትር ማሪያኖ ራሆይ በትምርታቸው፡በግርማ ሞገሳቸው ይመሰገናሉ።ውሸታም አይደሉም።

 

ጠቅላይ ሚኒስትሩ መናገር ያለባቸውን ነገር የዋጡ ቴክ ሬኮርደር።ለሁሉም የውጭ ጋዜጠኛ አንድ ዘፈን ያሰማሉ:: ሽብር ጸረ ሽብር፤የጸረ ሽብር ህጋችንን ከእግሊዝ ቀዳነው።የዲሞክራሲ ጀማሪዎች ነን

አንዳርጋቸው ጽጌ የእንግሊዝ ዜጋ ነው። ሁለተኛ ዜጋ ቤሆንም

 

አንዳርጋቸው ጽጌ የኤርትራ የትሮይ ፈረስ (ሰርጎ ገብ ነው)የታሰሩ ጋዜጠኞች ሽብርተኞች ናቸው።ዲሞክራሲ ሂደት ነው

 

እነበረከት ስሞን በጡረታ የወጡ መስለው አሻንጉሊት ተጫቃቾችን ምሳሌ ሀይለማርያም (የሟቹን መለስ ማሊያ ለብሶ የሚጫወተውን)ሬድዋን ሁሴን አሜሪካ መጥቶ ከባድ ስብራት ደርሶበት የነበረውን ከመጋረጃ ኋላ ሆነው እየዘወሩ በጫወታው ተካፍለዋል። ሺመልስ ከማል ጫት በብዛት እየቃመ ከጥቅም ውጭ በመሆኑ በዚህ ግጥሚያ አልተሰለፈም።

ይሄው እንግዲህ ደርግ ከሄደ አንስቶ ዲሞክራሲ እየተባለ ከበሮ ሲደለቅ ሃያ ዓመታት አልፋዋል።የኛስ ዲሞክራሲ ላሳር ነው። ማደግ እምቢ ያለ ድውይ ሆነ።ሸፍጥ፤ተንኮል እንዳያድግ የያዘው መልካም ነገር። እንደኔ እምነት ወያኔ ኢህአዴግ ሳይጫነቅ ህዝብን አክብሮ በሰላማዊ መንገድ የስልጣን ሽግግርን ያደርጋል ብሎ ማሰብ ሁኔታውን በቅጡ አለማስላት ነው።አምላክ የታረቃት አገራችን ወጣት ልጆችዋ ጠላትዋን ሊያጫንቁት ቆርጠል።ወያኔ ኢህአዴግ ይህን ስሙን አትጥሩባኝ ብላል።ካሁኑ ጨንቆት!

 

የፖለቲካ እስረኞች ይፈቱ!ምርጫ ከመካፈል በፊት ይህ ይቀድማል።

ኢትዮጵያ በክብር፤በአንድነት፤ተረጋግታ በነጻነት ትኖራለች።የጃዙር ቅኝ ግዛት አትሆንም!!!

_______________

ስለኢሳት

የኢሳት፡ቡድን ስለምርጫው በሚያቀርባቸው ዜናዎች ሊመሰገን ይገባል። የሁሉም የፖለቲካ ሀይሎች መቀራረቢ መድረክ መሆኑ ትልቅ ተስፋ ነው።

The post የስፓኙ ፓዴሞስ እና ኢትዮጵያ ህወያት\ኢህአዴግ::ዘጠኝ  ለዜሮ ተለያዩ appeared first on Zehabesha Amharic.

↧

መድረክ የእሁዱን ምርጫ ውጤት አልቀበልም አለ ‪

$
0
0

ምርጫ ቦርድ በዛሬው እለት ያወጣው ጊዜያዊ ውጤት ተቀባይነት የለውም ሲሉ የመድረክ ፓርቲ አመራር ፕሮፌሰር በየነ ጴጥሮስ ለቢቢኤን ገለጹ::
beyene_petros
የመድረክ ከፍተኛ አመራሮች ዛሬ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ፥ በምርጫው ሂደት ላይ ችግሮች የነበሩ በመሆኑ ውጤቱን አንቀበልም ብለዋል። አፍንጮ በር አከባቢ በሚገኘው የመድረክ ዋና ፅህፈት ቤት መግለጫ የሰጡት የመድረክ የወቅቱ ሊቀመንበር ፕሮፌሰር በየነ ጴጥሮስ ፣ ዶ/ር መረራ ጉዲና እና ሌሎች የመድረኩ አመራሮች ናቸው።

ምርጫ ቦርዱ በዛሬው እለት ይፋ ባደረገው ጊዜያዊ የምርጫ ውጤት መግለጫ ኢህአዴግ 100 ፐርሰንት በደረሱ ጊዜያዊ ውጤቶች ማሸነፉን ገልጽዋል፡፡ ከፍተኛ የህዝብ ድጋፍ ያለው መድረክ በበኩሉ በዛሬው እለት በሰጠው አስቸኳይ መግለጫ ይህንን እንደማይቀበለውና በምርጫው ጊዜ የደረሱትን ችግሮች በመዘርዘር ለሁለት ሰአታት መግለጫ ሰጥቷል፡፡

The post መድረክ የእሁዱን ምርጫ ውጤት አልቀበልም አለ ‪ appeared first on Zehabesha Amharic.

↧
↧

የአሜሪካ መንግስት ምርጫውን አሽሟጠጠው

$
0
0


ወያኔን በጓንትነት የሚተቀመው የአሜሪካ መንግስት በተቃዋሚ የለውጥ ሃይሎች ላይ በሲቭል ሶሳይቲ በነጻ ሚዲያዎች እና በነጻነት ድምጾች ላይ የሚደረገው ወከባ እንደሚያሳስበው በመግለጽ የአሜሪካ መንግስት ዲፕሎማቶች ምርጫውን እንዳይታዘቡ መከልከሉንና መደረጉን በለሆሳስ አንስቶ ከአፍሪካ ሕብረት ታዛቢዎች ያገኘውን መረጃ ዋቢ በማድረግ የተቃአሚ ሃይሎች ታዛቢዎች በምርጫው ላይ እንዳይታዘቡ መደረጉ እንዳሳዘነው በመግለጽ በምርጫው ወቅት የነበረው የአፍሪካ ሕብረት ታዛብ ቡድን እንኳን የወከባዎች ተጋሪ እንደነበር ተናግሯል መግለጫው::
election
ለፍትሃዊ እና ነጻ ምርጫ አስፈላጊ የሆኑ ነጻ እና ለቅስቀሳ የሚሆን የመረጃ ማሰራጫ ሚዲያ የዲሞክራሲ እና የሰብአዊ መብቶች ሲቭክ ማህበራት እንዲሁም የተላያዩ አለም አቀፍ እና ሃገር አቀፍ ሕብረተሰቦች በታዛቢነት ባልተወከሉበት ምርጫ ማካሄድ አያስኬድም ሲል መግለጫው አሽሟጧል::ጋዜጠኞችን በማሰር እና በማሳደድ የበጎ አድራጎት ድርጅቶችን ገደብ በመስጠት የፖለቲካ ድርጅቶች ውስጥ ጣልቃ በመግባት የፖለቲካ ምህዳሮችን በማጥበብ ምርጫ ማካሄድ አይሞከርም ሲል መግለጫው ተናግሯል::

የአሜሪካ መንግስት ከኢትዮጵያ እና ከሕዝቧጋር ጠንካራ ግንኙነት አለው ያለው መግለጫው ዲሞክራቲክ ተቋማት ዕንዲጠናከሩ የፕሬስ ነጻነተ እንዲያብብ በሃገሪቱ የታፈነው የፖለቲካ ምህዳር ሁሉ ክፍት እንዲሆኑ ኢትዮጵያ የፈረመችውን የአለም አቀፍ ሰባዊ መብቶች ድንጋጌ ግዴታዎች እንድታከብር አብረን እንሰራለን ብሏል::

The post የአሜሪካ መንግስት ምርጫውን አሽሟጠጠው appeared first on Zehabesha Amharic.

↧

የሳምንቱ ማስታወሻ – ኤርሚያስ ለገሰ

$
0
0

እሁድ ግንቦት 16 ቀን 2007
” እናት ሬስቶራንት” አሌክሳንድሪያ
እሁድ ምሳ ሰአት ላይ አትላንታ የሚገኘው ማህደር ሬዲዬ አዘጋጅ የሆነው አቶ ሰይፋ ደወለልኝ። በቀጥታ እየተላለፈ ባለው ፕሮግራማቸው ላይ አጫጭር ጥያቄዎች ስላሉት ሊጠይቀኝ እንደሚፈልግ ገለፀ። አጭር ከሆነ ለመመለስ ፍቃደኛ መሆኔን ነገርኩት።
” በዛሬው ምርጫ የወያኔ መንግስት ለተቃዋሚዎች ስንት ወንበር የሚለቅላቸው ይመስልሀል?” በማለት ጠየቀኝ።
ብዙም ማሰብ ሳይጠይቀኝ፣ ” ምንም ወንበር አይሰጣቸውም!” አልኩት። መልሴ ብዥታ የፈጠረበት ስለመሰለኝ ምክንያት ያልኩትንም ጨምሬ ለማስረዳት ሞከርኩ። ከማህደር ሬዲዬ ጋር የነበረን ቃለምልልስ ሲጠናቀቅ “በእናት ሬስቶራንት” ምሳ የጋበዘኝ ጋዜጠኛ ወዳጄ በአስተያየቴ አለመስማማቱን ነገረኝ። አገርቤትን የሚያስታውስ ክትፎ መመገብ ትቶ ይሞግተኝ ጀመር። በስስት የሚቀርበውን ቆጮ የምሻማበት ጊዜ በማግኘቴ ወጉን እንዲቀጥል አደረኩ። እንዲህ በማለት ጀመረ፣
ermias copy
” ለማየት ያብቃህ እስከ ሀያ ወንበር ይፀድቁባቸዋል። ለሰማያዊ 2፣ ለመራራ ፓርቲ እስከ 15፣ ለበየነ እስከ 3 ወንበር ይሰጧቸዋል። ከጀርባቸው ቢታረዱ ሰባራ ወንበር የማይሰጡት ለገብሩ አስራት ፓርቲ ነው” አለኝ።
” ሌሎቹም ፓርቲዎች ከአረና ፓርቲ የተለየ እጣ ፋንታ አይደርሳቸውም” አልኩት።
” እንዴት?፣ ለምን? መነሻህ ምንድነው?” በጥያቄ አጣደፈኝ። ድሮም የጋዜጠኛ ነገር!
” የህውሀትን ባህሪ በደንብ መረዳት ያስፈልጋል። የህውሀት ባለስልጣናትና ካድሬዎች አስተሳሰብ፣ ባህሪ፣ እምነትና ተግባር ጠንቅቆ ማወቅ የስርአቱን ምንነት ለመረዳት እድል ይሰጣል። ሲጀምር ህውሀት የበታችነት ስሜት የተጠናወተው ድርጅት ነው። በዚህ ምክንያት ቀንና ለሊት የፍርሀት ማእበል የሚንጠው ነው። በሁለተኛ ደረጃ ህውሀት እወክለዋለው ብሎ የሚያስበው ህዝብ ከኢትዬጲያ ህዝብ ከ7% በታች ስለሆነ የስልጣኑ ምንጭ ዲሞክራሲያዊ በሆነ መንገድ በሚካሄድ ምርጫ አይደለም። ይልቁንስ ህዝብን የመግዛት ሌጅትመሲው የሚመነጨው በዘረጋው የፀጥታ መዋቅርና የጠመንጃ አፈሙዝ ነው። በሶስተኛ ደረጃ ሁሉን የጠቀለለ ስልጣን ፍላጐት የሚመነጭ ነውር የማያውቁ ስግብግቦች ናቸው። አንዲትም ቀዳዳ መክፈት አይፈልጉም። በዛ ላይ ልባቸው አይገኝም” አልኩት።
” ልባቸው አይገኝም ስትል ምን እንዳስታወስከኝ ታውቃለህ? አስመራ የሄድኩ ጊዜ አንድ እጅግ ጠመዝማዛ ፣ በጣም ረጅምና የሚያስፈራ መንገድ ጐብኝቼ ነበር። ”
ንግግሩን አቋርጬው ፣
” ከሊማሊሞ ይብሳል?” አልኩት። በአንድ ወቅት አቶ መለስ ተቃዋሚዎችን ሲያስፈራራ የሊማሊሞን መንገድ ማንሳቱ ትዝ ብሎኝ።
” ሊማሊሞን አላውቀውም። ኤርትራ እንዳየሁት ጠመዝማዛ መንገድ ከሆነ ግን በጣም ያስፈራል። …እናም የገረመኝ ምኑ መሰለህ? የመንገዱ ስያሜ!”
” ምንድነው የሚባለው?”
አንገቱን አየነቀነቀ ” ልበ-ትግራይ ” አለኝ።
” አውቃለሁ አልኩት ” ርግጥም አውቅ ነበር። አስከትዬም “ታዲያ ጃንሆይ በዚህ መንገድ ላይ ከኤርትራውና ከትግራዩ ገዥ ጋር ሲሄዱ የተበሻሸቁትን አልነገሩህም?” አልኩት።

” አልነገሩኝም!” አለ ጆሮውን አቁሞ።
” እንዳትናደድ ብለው ነው። ለማንኛውም ሌላ ጊዜ አጫውትሀለሁ። አሁን ቅድም ወደ ጀመርነው የምርጫ አጀንዳ እንመለስ። …ህውሀቶችን እስከማውቃቸው ድረስ ሁሉን ካልጠቀለሉ እንደ ውርደት የሚቆጥሩ ናቸው። በዛ ላይ ተቃዋሚዎችን ” ጠላቶች”፣ ” እንቅፋቶች”፣ ” የጥፋት ግንባሮች” በሚል የማጭበርበሪያ ስትራቴጂ የሚፈርጁ ናቸው። እንደዚህ አይነት አመለካከት ኖሯቸው ወንበር ይለቃሉ ማለት ከእባብ እንቁላል እርግብ የመጠበቅ ያህል ነው” አልኩት።
” እኔ እኮ ይሄ አዳፋና እኩይ ባህሪያቸው ጠፍቶኝ አይደለም። ግን ቢያንስ ምእራባውያንን ለማስደሰትና እርዳታና ብድር ለማግኘት የተወሰነ ወንበር ሊለቁ ይችላሉ ከሚል ምልከታ ተነስቼ ነው።”
” የኢሳቱ ብእረኛ ገብረጳዲቅም እንደዛ አይነት ሀሳብ ያለው ጵሁፋን አዳምጫለሁ። እነዚህ ሰዎች የለከፋቸው የጠባብነት ደዌ ወደ ካንሰር ከተቀየረ ቆይቷል። ከድሮ አስተሳሰባቸው መላቀቅ አይችሉም። እንደውም የመራራን ቃል ልዋስና ‘ ጫካው ከእነሱ ወጣ እንጂ፣ ‘እነሱ ከጫካው አልወጡም ‘ … ከተጣባቸው የዜሮ ድምር ፓለቲካ መላቀቅ አይችሉም” በማለት ምላሽ ሰጠሁት።
” አንተ ያልከው ከሆነ አሜሪካንን ጉድ አደረጓት። በተለይ የውጭ ጉዳይ መስሪያቤቱና በዲሞክራሲያዊ መንገድ የተመረጠ መንግስት ብላ የተናገረችው ሴትዬ ምን ይውጣታል? እውነቴን ነው የምልህ! ስቴት ዲፓርትመንቱ አመታዊ ሪፓርቱን ሲያወጣ ምን ብሎ ሊጀምር ነው? ” በዲሞክራሲያዊ መንገድ የተመረጠው የኢትዬጲያ መንግስት…” ብሎ ሊጀምር ነው?” በማያቋርጥ ሳቅ ውስጥ ሆኖ ተናገረ።

” አየህ! አሜሪካኖቹ ብዙ የገባቸው የማይመስለኝ ህውሀት አሜሪካንን ማዋረድ እንደ አንድ ዋነኛ ስራው ከወሰደ መቆየቱን ነው። ለዚህ የተለያየ ምክንያት አላቸው። ሲጀመር አሜሪካኖች ስታዋርዳቸውና ፊትህን ስታዞርባቸው ይቀርቡሀል የሚል አመለካከት አላቸው። ሲቀጥል በምስራቅ አፍሪካ የአሜሪካን ፍላጐት ወታደራዊ ድጋፍ ማግኘት ነው። ይህን ፍላጐት ያለማቅማማት ማሟላት የሚችሉት እነሱ እንደሆነ ጠንቅቀው ያውቃሉ። ለዚህም ነው በብዙ ኢትዬጲያውያን ዘንድ የሱማሊያ ጦርነት ” ለአሜሪካን ቀብድ ማስያዣ የተደረገ የውክልና ጦርነት” የሚል ስያሜ የተሰጠው። በነገራችን ላይ ከኢትዬጲያ አንጳር የአሜሪካ ወታደራዊ አታሼዎቹ ከውጭ ጉዳይ መስሪያቤቱ በላይ ስልጣን እንዳላቸው ህውሀቶች ያምናሉ። ሌላው ቀርቶ በቅርቡ የሳሞራ የኑስ ወደ አሜሪካ መምጣት ለምን እንደሆነ መገመት ትችላለህ” አልኩት።
” እና አሜሪካን የምርጫ ውጤቱን ትቀበለዋለች ብለህ ታስባለህ?”
” ብትቀበለውም/ ባትቀበለውም ለራሷ ጥቅም ስትል ከህውሀት መራሹ መንግስት ጋር እጅና ጓንት ሆና ለተወሰነ ጊዜ ትቀጥላለች።”
” እስከመቼ?”
” የሐይል ሚዛኑ እስኪያጋድል ድረስ!”
***
ግንቦት 18 ቀን 2007, ክሪስታል ሲቲ
አሜሪካኖቹ የነጳነት ቀናቸውን እያከበሩ ነው። ስራ ተዘግቷል። ዋሽንግተን ዲሲ ከየግዛቱ በመጡ ሞተረኞች ተጨናንቃለች። አንዳንድ የቀለበት መንገዶች ተዘግተዋል። መዝናኛዎች እስከ አፍጢማቸው ሞልተው ህዝቡ እደጅ ፈሷል። እኛም ወጉ አይቅርብን ብለን የአሜሪካኖቹን የነጳነት ቀን ለማክበር ከጋዜጠኛው ጓደኛዬ ጋር ወደ ክሪስታል ሲቲ ተያይዘን ሄደናል። አላማችን የአሳዳሪዎቻችንን የነጳነት ቀን ለመዘከር ቢሆንም ወጋችን በሙሉ በብዙ ሺህ ማይሎች ተጉዞ የሀገራችን ሁኔታ ላይ አርፋል። ውጤቱ አስቀድሞ የሚታወቀው ምርጫ!! እውነት ለመናገር ለምርጫው ሂደት ትኩረት ያልሰጠው የኢትዬጲያ ህዝብ በየቦታው በሚሰማው የሰማይና የምድር ልዩነት ያለው ውጤት እጅግ መገረሞች ታይተዋል። የህውሀት ንቀት መረን ማጣቱ ብዙ ኢትዬጲያውያንን አስቆጭቷል። በማህበራዊ ድረገጶችም መወያያ የሆነው ይህ ለከት ያለፈው የህውሀት ነውረኝነት መሆኑ አልቀረም።
ቀኑን ሙሉ መረጃ ሲሰበስብ የዋለው ጋዜጠኛ ወዳጄ የነበረው ፊት መገረሙን የሚያሳብቅ ነበር። ንግግሩንም የጀመረው እሱ ነበር፣
” የአፍሪካ ህብረት ታዛቢ ያለውን ሰማህ?” በማለት ጠየቀኝ።
” ለምንድነው የምንሰማው?… መጀመሪያውኑ የሟሸሸና ለይስሙላ የመጣ ነው። በሀገሪቱ ኢህአዴግ ያዘጋጃቸው ምርጫ ጣቢያዎች ከ45,000 በላይ ናቸው። የአፍሪካ ታዛቢዎች ማዳረስ የቻሉት 356 ጣቢያዎች ብቻ ነው። ይህ ማለት በአጠቃላይ ማዳረስ የቻሉት ከአንድ ፐርሰንት በታች (0•8% ) ብቻ ነው። መሰረታዊ የስታስቲክስ ናሙና ጥናትን ገደል የከተተና ተቀባይነት የሌለው ነው። በዛ ላይ እንደ አፋር ያሉ ምርጫው ከመካሄዱ በፊት ኮሮጆ የሚጠቀጠቅባቸው ቦታዎች ታዛቢ አላኩም” በማለት ምላሽ ሰጠሁት።
” ቢሆንም ባልተለመደ ሁኔታ ከተመለከቷቸው ቦታዎች 21% ኮሮጆዎች ቀድመው ህጉ ከሚፈቅደው በፊት ተከፍተው አይተናል ማለታቸው ትልቅ ጅምር ነው። በዛ ላይ ምርጫው ፍትሀዊ፣ ዲሞክራሲያዊ፣ ነጳ የሚሉ ቃላትን ከመጠቀም ተቆጥበዋል። ይህ ለህውሀት መጥፎ ምልክት ነው” በማለት ከሰበሰበው መረጃ በመነሳት ተናገረ። አስከትሎም፣
” ይልቁንስ አስገራሚ ውጤቶች ልንገርህ። ሀይለማሪያም ደሳለኝ በተወዳደረበት በሎሶ በምትባል ምርጫ ክልል 100% ሲያገኝ፣ የሰማያዊና ኢራፓ ፓርቲ እጩዎች 0% አግኝተዋል። ” በማለት እፍረት አፋን ሞልቶት ተናገረ። እኔም ከአፋ ተቀብዬ፣
” ባይሆን ነበር የሚገርመኝ። ጋሽ ሀይሌ እኮ በልቡ አቶ መለስን አስቀምጦ ነው የሚንቀሳቀሰው። እሱ ያደረገውን ማድረግ አለበት። እሱ የተናገረውን መናገር አለበት። ቀድሞ አቶ መለስ እንደሚያገኘው አህያ የማይሸከመው ድምጵ ማግኘት አለበት። በአካባቢው ያለውን ተቀባይነት በመቶ ፐርሰንት ካላሳደገ ሌላው ጋር ያለው ክብር ወደ ታች ይወርዳል ብሎ ማሰቡ አይቀርም። ጋሽ ሀይሌ ለህዝብ በሚታይ ችሎታው ተፈትኖ ሰለወደቀ ያለችው ብቸኛ አማራጭ ይህቺ ብቻ ናት። አማኑኤልና ጋዜጠኛ ወንድሙ ይህን ተልእኮ የፈፀሙ ይመስለኛል” አልኩት።
” ሆዳሙ በሬ?”
“በነገራችን ላይ ከማን አንሼ በሚመስል መንገድ አማኑኤል አብርሀ ( ኢህአዴግ ቢሮ) በወላይታ አንድ ምርጫ ክልል 1182 ሲያገኝ ተቀናቃኙ አንድ ድምጵ ብቻ እንዲያገኝ አድርጓል። የሚገርምህ በምርጫ 97 አማኑኤል የወላይታ ህዝብ ይጠላዋል ብሎ በረከት በመጨረሻው ሰአት ጋሽ ሀይሌን ትእዛዝ ሰጥቶት እንዲሰረዝ ተደርጓል።
” ታዲያ ዛሬ ለውድድር ሲቀርብ ህዝቡ ተሳስቶ ነበር ማለት ነው? ወይንስ በረከት ተደቆሰ?”
” እሱ ጊዜ ይፈታዋል። ከዛ ይልቅ ህዝቡ ተሳስቶ ነበር የሚለውን እንቀበል! አይመስልህም?” አልኩት።
” ህዝብማ መሳሳቱን እማ በፕሮፌሰር በየነ ድምጵ አሳዩን። እስቲ እግዜር ያሳይህ የሾኔ ህዝብ ” በየነ ክብራችን” የሚል ዘፈን ያለው ህዝብ ነው። ሾኔ ስለበየነ ክብርና ዝና አውርታ የምትጠግብ አይደለችም። በእሱ መማል ብቻ ነው የሚቀራቸው። በነገራችን ላይ ብዙ ልጆች ስማቸው በየነ ነው። እንደዚህ በምታከብረው ወረዳ ዬሴፍ ዳይሞ የሚባል ማንም የማያውቀው የኢህአዴግ ተወካይ 10,961 ሲያገኝ በየነ 252 አገኘ ብሎ ማወጅ አሳፋሪ ነው። ቢገባው ለሀይለማርያም ራሱ ውርደት ነበር? ”
” ሀይሌ ከተዋረደ ቆየ እኮ!” የለበጣ ሳቁን ለቀቀው።
” ለነገሩ ጋሽ ሀይሌ መቼ እንደበቃኝ ታውቃለህ? አንድ ጊዜ በድሬደዋ የሀገር ሽማግሌዎችን ለማነጋገር ወደ ድሬ ያቀናል። ሽማግሌዎቹ አርብቶ አደሮች ስለነበሩ በርካታ ግመሎች አላቸው። በጥያቄና መልስ ጊዜ በድሬደዋ የተሰራው ድልድይ አጭር ስለሆነ ግመሎቻቸውን ማሳለፍ እንደቸገራቸው ይነግሩታል። ምን ብሎ ምላሽ የሰጠ ይመስልሀል?”
” ምን አለ በእናትህ?”
” ፕላኑን የሰሩት ቻይናዎች ስለሆኑ የግመል ቁመት ስንት እንደሆነ አያውቁም። ኢትዬጲያዊ መሀንዲሶቹም ከደጋ አካባቢ ስለመጡ የግመል ቁመት አያውቁም።”
***

The post የሳምንቱ ማስታወሻ – ኤርሚያስ ለገሰ appeared first on Zehabesha Amharic.

↧

“ምርጫው ተብዬውን ቧልት ላለመታዘብ ወሰንን”–አና ጎምሽ

$
0
0

የዘንድሮው ኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ተካሄደ፡፡ የምርጫውን ሂደት የታዘበው ብቸኛ ዓለምአቀፍ ተቋም የአፍሪካ ኅብረት ነው፡፡
The Honorable Ana Gomes blasts EU over human rights violations in Ethiopia (video)
ለወትሮ የኢትዮጵያን ምርጫዎች ይታዘቡ የነበሩትና አሁንም በዓለም ዙሪያ እየተንቀሣቀሱ የሚታዘቡት የአውሮፓ ሕብረትና የአሜሪካው የካርተር ማዕከል ግን አልተገኙም፡፡ ለምን?

የአውሮፓ ፓርላማ አባል የሆኑትና የ1997ቱ ምርጫ የኅብረቱ የታዛቢዎች መሪ የነበሩት አና ጎምሽ የአውሮፓ ኅብረት ያልታዘበው ምርጫው “ቧልት ስለሆነ ነው” ብለዋል፡፡

“የአውሮፓ ኅብረት የታዛቢዎችን ቡድን በመላክ ለገዥው ፓርቲ ዲሞክራሲያዊ ምርጫ ያካሄደ የማስመሰያ ማኅተም መስጠት ስላልፈለግን የደረስንበት የፖለቲካ ውሣኔ ነው” ብለዋል፡፡

ለመሆኑ የኢትዮጵያ መንግሥት አሁን ባለው አቋሙ ዴሞክራሲያዊ፤ ፍትሐዊና ነፃ ምርጫ ለማካሄድ ብቁ ነው?

“አይደለም ብሎ የሚያሣምነኝ እስካልመጣ፤ አዎ ብቁ ነው” ይላሉ በደቡብ ሱዳን የፕሬዚዳንት ሳልቫ ኪር ልዩ አማካሪ እንዲሆኑ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የላካቸው፤ በዩናይትድ ስቴትስ የተወካዮች ምክር ቤት የአፍሪካ ስፔሻሊስት ሆነው ለሃያ አራት ዓመታት ያገለገሉት አቶ ቴዎድሮስ ዳኘ፡፡

“ኢትዮጵያ ውስጥ የፖለቲካ ችግር አለ የሚባል ከሆነ ብዙውን ጊዜውን እርስ በራሣቸው በመጣላትና በውጭ ሃገሮች በመኖር ጊዜያቸውን የሚያጠፉት ተቃዋሚ ፓርቲዎችም ተጠያቂነቱን ሊወስዱ ይገባቸዋል” ብለዋል አቶ ቴዎድሮስ፡፡

ለተጨማሪ ከሁለቱም ጋር በተደረጉ ቃለምልልሶች ላይ የተዘጋጀውን ቅንብር የያዘውን የተያያዘውን የድምፅ ፋይል ያዳምጡ፡፡

The post “ምርጫው ተብዬውን ቧልት ላለመታዘብ ወሰንን” – አና ጎምሽ appeared first on Zehabesha Amharic.

↧

Sport: የአለምነህ ዋሴ ትንታኔ: 7 የፊፋ አልቅቶች(ሙሰኞች) ስዊዘር ላንድ ውስጥ ታፈሱ

↧
↧

አሜሪካ ውስጥ ርካሽ እና ውድ የቤት ኪራይ ያለባቸው ከተሞች ተለይተው ታወቁ

$
0
0

(Admas Radio)
ካሊፎርኒያ፣ ዋሽንግተን ዲሲ፣ ሃዋይ፣ ኒውዮርክ እና ኒውጀርሲ ውድ ቤት ኪራይ ያለባቸው ከተሞች መሆናቸውን ሰሞኑን የወጣ ሪፖርት አሳይቷል።
new-york-city
አንድ በኒውጀርሲ ከተማ ለመኖር የፈለገ ተከራይ ባለሁለት መኝታ ቤት ተከራይቶ ለመኖር አንድ በሰዓት 25 ዶላር የሚከፈልበት የሙሉ ሰአት ሥራ መስራት ይኖርበታል። በኒውጀርሲ በአማካይ የሁለት መኝታ ቤት ዋጋ 1300 ዶላር በወር ነው። አንድ ሰው የቤት ክፍያው ከደሞዙ ከ 30 በመቶ መብለጥ አይኖርበትም – አቅም አለው ለመባል። በዚህ መሰረት 1300 በወር ከፍሎ ለመኖር ቢያንስ በወር አንድ ሰው 4ሺ 500 ዶላር ገቢ ሊኖረው ይገባል።

በኒውጀርሲ የቤቶችና ማህበረሰብ እድገት አጥኚ የሆኑት አርኖልድ ኮህን በርካታ የአሜሪካ ግዛቶች ነዋሪዎቻቸው ሁለት መኝታ ቤት አፓርትመንት የመከራየት አቅም እንዲኖራቸው የሚያስችል ክፍያ የላቸውም ይላሉ። በተለይ የኒውጀርሲን ሲያስረዱ “ልጆቻችንን የሚጠብቁልን፣ አዛውንቶቻችንን የሚንከባከቡልን፣ ግሮሰሪና ሌላም ቦታ የሚያስተናግዱን፣ ለየለት ለት ጉዳዮቻችን ተስፋ የምንጥልባቸው ሁሉ ፣ ለራሳቸው መኖሪያ ለመክፈል ግን አይችሉም” ሲሉ ይናገራሉ።

በኒውጀርሲ ግዛት መካከለኛ የሰአት ክፍያ 17 ዶላር ሲሆን፣ በሰአት 17 ዶላር የሚከፈለው ሰው ፣ ሁለት መኝታ ቤት አፓርትመንት መከራየት እንዲችል በሳምንት ቢያንስ 59 ሰአት መስራት ይኖርበታል። የግዛቱን ዝቅተኛ የሰአት ክፍያ ማለትም 8.38 ዶላር በሰ አት የሚከፈለው ሰው ሁለት መኝታ ቤት ካማረው ሶስት የሙሉ ሰአት ሥራ ያስፈልገዋል። ያ ማለት ደግሞ 24 ሰአት በቀን መስራት አለበት ማለት ነው።

በአንዳንድ የኒውጀርሲ አካባቢዎች ፣ ለምሳሌ በሃንተርደን፣ ሚድልሴክስ እና ሶመርሴት አካባቢዎች ሁለት መኝታ ቤት እስከ 1500 ዶላር ይደርሳል። በአንጻሩ በሱሴክስ፣ ኬፕ ሜይ እና ግላክስተር የሚባሉ ካውንቲዎች ኪራዩ የሚቀንስ ቢሆንም፣ በዚያ አካባቢ የሚኖሩ ደግሞ በአብዛኛው በሰአት 10 ዶላር አካባቢ የሚከፈላቸው ናቸው።

ለዚህም ነው ባሳለፍነው ሳምንት በኒውጀርሲ የሚገኙ ግለሰቦችና ድርጅቶች ፣ እንደ ሰዉ አቅም የሚሆኑ ቤቶች እንዲሰሩ ግፊት የሚያደርግ ስብሰባ ያካሄዱት: በዚህ ስብሰባ የኒውጀርሲ ባለሥልጣናት ሁሉም እንዳቅሙ የሚኖርባቸው ቤቶች እንዲሰሩ ጥያቄ ቀርቦላቸዋል።

በኒው በርንስዊክ ከተማ ነዋሪ የሆነው ፖል ሜየርስ በወር 1500 ዶላር እየከፈለ በተከራየው ሁለት መኝታ ቤት አፓርታማ ከቤተሰቦቹ ጋር ይኖር ነበር። በመካከል ይስራ የነበረው የሽያጭ ሥራ ተቋረጠ። ለቤት ኪራይ የሚከፍለውም አጣ። በዚህ ጊዜ የቤት ዕቃዎቹን እያወጣ መሸጥ ነበረበት። “እንደዚያም ሆኖ መኖር አልቻልኩም፣ የምሸጠው አለቀ፣ የቤት ኪራይ ግን እየጠበቀኝ ነበር” ነው ያለው።
ከዚያ በኋላ ምርጫ አልነበረውም ከነቤተሰቡ ወጥቶ በመቆያ ጣቢያ (ሼልተር) መኖር ጀመረ። ስምንት ወር እዚያ ከቆየ በኋላ እሱ ሚስቱና አንድ ልጁ ከዚያ ወጥተው ኪልመር ሆምስ የተባለው ድርጅት በመንግስት ድጋፍ በሚገነባቸው አፓርታማዎች መኖር ጀመረዋል። እነዚህ አፓርታማዎች ሰዎች እንደገቢያቸው ልክ የሚከፍሉባቸው ናቸው። ሆነም ቀረ፣ ያቺንም ቢሆንም ለመክፈል ፖል ቀን ከሌሊት መስራት ነበረበት።

በሰሞኑ ጥናት መሰረት ውድ የአፓርታማ ኪራይ የተመዘገበባቸው ከተሞች መካከል ሃዋይ በቀዳሚነት ይጠቀሳል። በሃዋይ ሁለት መኝታ ቤት አፓርታማ 1700 ዶላር ሲደርስ፣ በዲሲ 1500 ዶላር አካባቢ፣ በካሊፎርኒያ 1389 ፣ በኒውርዮክ 1335፣ እንዲሁም ኒውጀርሲ 1309 ዶላር በአማካይ ናቸው።

በሌላ በኩል ርካሽ የሚባል ባለሁለት መኝታ ቤት አፓርታማ ከሚገኝባቸው ከተሞች መካከል ፖርቶሪኮ 547 ዶላር ፣ አርካንሳ 673 ዶላር ፣ ኬንታኪ 683 ዶላር፣ ዌስት ቨርጂኒያ 687 ዶላር እንዲሁም ሳውዝ ዳኮታ 698 ዶላር ይጠቀሳሉ።

The post አሜሪካ ውስጥ ርካሽ እና ውድ የቤት ኪራይ ያለባቸው ከተሞች ተለይተው ታወቁ appeared first on Zehabesha Amharic.

↧

ምርጫ ቦርድ የአስቂኙን ምርጫ ውጤት ይፋ አደረገ * ኢሕአዴግ 100% አሸነፈ አለ * ምንም አይነት ተቃዋሚ ፓርቲ የፓርላማ ወንበር አላገኘም

$
0
0

(ዘ-ሐበሻ) ኢህአዴግ እና አጋር ድርጅቶቹ የዘንድሮውን አሳፋሪ ምርጫ 100% ማሸነፋቸውን ምርጫ ቦርድ ይፋ ባደረገው ሪፖርት ገለጸ:: ምንም አይነት ተቃዋሚ ፓርቲ በፓርላማው ውስጥ መቀመጫ እንዳላገኘም ተገልጹዋል::
election board
የገዢው ፓርቲ መሳሪያና ገለልተኛ ያልሆነው ምርጫ ቦርድ ይፋ ባደረገው ሪፖርት ኢህአዴግ አዲስ አበባ ላይ ከ23 መቀመጫዎች ኢህአዴግ 23ቱንም መቀመጫዎች አግኝቷል።
– ከትግራይ ክልል ቦርዱ ከደረሱት የ31 መቀመጫዎች ውጤት ህውሃት/ኢህአዴግ 31 መቀመጫዎችን
– ከአማራ ክልል ከደረሱት የ107 መቀመጫዎች ውጤት ብአዴን/ኢህአዴግ 107 መቀመጫዎች
ከኦሮሚያ ክልል ቦርዱ ከደረሱት የ150 መቀመጫዎች ውጤት ኦህዴድ/ኢህአዴግ 150 መቀመጫዎችን
– በኢትዮጵያ ሶማሊ ክልል ቦርዱ ከደረሱት የ16 መቀመጫዎች ውጤት ኢሶዴፓ 16 መቀመጫዎችን
– ከቤንሻንጉል ጉሙዝ ክልል ከደረሱት የሰባት መቀመጫዎች ውጤት ሰባቱንም ቤጉዴፓ;
– ከደቡብ ክልል ከደረሱት የ95 መቀመጫዎች ውጤት ዴኢህዴን/ኢህአዴግ 95 መቀመጫዎች፣
– በጋምቤላ ክልል ጋህዴፓ ከሶስት መቀመጫዎች ሶስቱንም፣ በሀረሪ ክልል ሀብሊ ከ2 መቀመጫዎች አንዱን ሲያገኝ አንዱን ኦህዴድ/ኢህአዴግ፣
– በድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ከሁለቱ መቀመጫዎች አንዱን ኦህዴድ/ኢህአዴግ ቀሪውን ሶህዴፓ አግኝተዋል
– ከአፋር ክልል ከደረሰው ከደረሰው የስድስት መቀመጫዎች ውጤት አብዴፓ ስድስቱንም መቀመጫ አግኝቷል።

በአሳፋሪነቱ የሚጠቀሰው የዘንድሮውን ምርጫ የአውሮፓ ሕብረት; የአሜሪካ መንግስትና ሌሎች ዓለም አቀፍ ድርጅቶች ፍትሃዊ ያልሆነ ምርጫ ሲሉ አውግዘውታ:: ተቃዋሚዎችም የምርጫውን ውጤት እንደማይቀበሉት አስታውቀዋል::

The post ምርጫ ቦርድ የአስቂኙን ምርጫ ውጤት ይፋ አደረገ * ኢሕአዴግ 100% አሸነፈ አለ * ምንም አይነት ተቃዋሚ ፓርቲ የፓርላማ ወንበር አላገኘም appeared first on Zehabesha Amharic.

↧

ግንቦትና ግንቦታውያን

$
0
0

– ከጌታቸው ሽፈራው
ግንቦት በሞቃታማው በጋ እና በክረምቱ መካከል የሚገኝ የሙቀትና የወበቅ ወር ነው፡፡ ይህ ወር አየር ንብረቱ በቅጡ የማይታወቅ፣ ሙቀትና ቅዝቃዜ የሚፈራረቅበት እንደመሆኑ ለሰዎች ጤና ተስማሚ አይደለም፡፡ ሙቀትና ቅዝቀዜው ድብልቅልቅ ባለበት በዚህ ወር አብዛኛው አርሶ አደር በበሽታ ይጠቃል፡፡ በዝናብ እጥረትና በረዥሙ በጋ ምክንያት ከብቶቻቸው ያልቃሉ፡፡ በአጠቃላይ ግንቦት ለአብዛኛው ኢትዮጵያውያን የመከራና የስቃይ ወር ነው፡፡
mengistu hailemariam
ይህንንም ተከትሎ ኢትዮጵያውያን ወሩን መልካም ነገር ይዞ እንዲመጣ አምላካቸውን ይማጸናሉ፡፡ ለአብነት ያህል ክርስቲያኖችና የሌሎች እምነት ተከታዮችም የግንቦት ልደታ ዕለት (አብዛኛዎቹ ከእምነት ይልቅ አምልኮ አዊ ያደርጉታል) ንፍሮ አንፍረው፣ ቡና አፍልተው የግንቦት ወር ጦስ በጭስና በንፍሮ ውሃ ለመሸኘት ይጥራሉ፡፡ ሆኖም ግን ለኢትዮጵያውያን ግንቦት የመከራ ዘመን፣ የደም ወር ከመሆን አላለፈም፡፡ ከዚህ ወር ጦሶች መካከል ለአሁኑ ዘመን መከራ ምንጭ የሆኑትን ግንቦታዊ ክስተቶች ብቻ እጠቅሳለሁ፡፡

26 አመታትን ወደኋላ ስንመለስ ኢትዮጵያ ለአሁኑ ፖለቲካዊ፣ ጂኦ ፖለቲካዊና ሌሎች አሉታዊ ገጽታዎች የዳረጋትን ውጥንቅጥ እናገኛለን፡፡ ግንቦት 8/1981 ዓ.ም፡፡ ይህ ወቅት የኢትዮጵያ ወታደሮችና አመራሮቻቸው በጦርነት የተማረሩበት ወቅት ነበር፡፡ ከጀኔራሎቹም በላይ በእነ መንግስቱ ኃይለማርያም ይሁንታን ያገኘ ካድሬ ስለ ወታደራዊ ስትራቴጅ ለመተንተን የሚቃጣበትና ጀኔራሎቹን ያማረረበት ወቅት እንደነበር በርካቶች እማኝነ ታቸውን ይሰጣሉ፡፡ በገፈፋና በግድ ጦር ሜዳ ይቀላቀሉ የነበሩ ወታደሮች በቁርጠኝነት ይዋጋ የነበረውን ሰራዊት መንፈስ ቀይረውታል፡፡ ይህ ሁሉ ውጥንቅጥ ያሳሰባቸው የጦሩ መሪዎች ኮሎኔል መንግስቱ ኃይለማርያም ከስልጣን ካልተወገዱ ኢትዮጵያ የገባችበት ችግር ሊፈታ እንደማይችል አመኑ፡፡ ‹‹በጓድ መንግስቱ ኃይለማርያም›› ላይ ይሞከራል ተብሎ የማይታሰበውን መፈንቅለ መንግስትም ወጠኑ፡፡ አዲስ አበባና አስመራም የመፈንቅለ መንግስት መሪዎቹ ማዕከል ሆኑ፡፡ ሆኖም የአዲስ አበባው ማታ ላይ እንዲሁም አስመራው ደግሞ ከአንድ ቀን በኋላ ግንቦት 8/1981 ዓ.ም ከሸፈ፡፡ አዲስ አበባ ውስጥ ሙከራውን ያደረጉት ጀኔራሎች ራሳቸውን ገደሉ፣ ተገደሉ፣ ታሰሩ፡፡ አስመራ ላይ ደግሞ ግንቦት 9 የ102ኛ አየር ወለድ ክ/ጦር በምስራቅና በሰሜን የገጠማትን ጦርነት ሲመሩ የኖሩትን ጀኔራሎች ዓይናቸ ውን ጎልጉሎ፤ በየጎዳናው እየጎተተ፣ አንገታቸውን ቆርጦ ብቻ ወታደር በመሪዎቹ ላይ ብቻ ሳይሆን ጠላት በማረካቸው ላይ ሊያደርገው በማይታሰበው አረመኔያዊ ድርጊት አስመራን የደም አላባ አደረጋት፡፡ በመፈንቅለ መንግስት በአጠቃላይ ከ137 በላይ የጦሩ አመራሮች ታሰሩ፡፡ ከእነዚህ መካከልም 28 ጀኔራሎች፣ 20 በላይ ኮሎኔሎች፣ 20 በላይ ሻለቃዎች፣ 20 በላይ ሻምበሎች ይገኙበታል፡፡ ገንጣይ አስገንጣይ የሚባሉት ሳይቀሩ አንዳንዶቹ ‹‹የኢትዮጵያ መንግስት ቀኝ እጁን በግራ እጁ ቆረጠ!›› ሲሉ ሌሎቹ ደግሞ ‹‹ኢትዮጵያ የጦር መሃንዲሶቿን ገደለች፣ በላች›› ብለው ጽፈውታል፡፡ በዚህ ምክንያት 270 ሺህ ያህል ኤርትራ ውስጥ የነበረው ሰራዊት አመራር አልባ ሆነ፡፡

መፈንቅለ መንግስቱ በከሸፈ በሁለተኛው ቀን ግንቦት 10 በርካታ የኢትዮጵያ ሰራዊት አመራሮች ሲገደሉ፣ ሲታሰሩና ከጦሩ ሲርቁ እንዲሁም ሰራዊቱም ሆነ አመራሩ ሞራሉ ሲላሽቅ ሻዕቢያና ህወሓት የኢትዮጵያን ሰራዊት ይዞት የነበረውን ሰፊ መሬት ማስለቀቅ ጀመሩ፡፡ ይህ ወቅት የኢትዮጵያ ሰራዊት እንደ ውጭ ወራሪ ያለ ርህራሄ የተጨፈጨፈበት ጊዜ ነው፡፡ ህወሓትና ሻዕቢያ የተማረከውን ሰራዊት ሳይቀር መሬት ላይ አስተኝተው በመድፍ ጨፍልቀውታል፡፡ ቁስለኛውን በጅምላ ሲፈልጉ ወደ ገደል፣ ሲፈልጉ ወደባህሩ አሊያም በጅምላ የጨፈጨፉበት ወቅትም ነው፡፡ ይህ ወር ኤርትራና ትግራይ በኢትዮጵያ ሰራዊት ደም የጨቀየበት ክፉ ቀን ነው፡፡
ይህ ግንቦት ያመጣው ጦስ የኢትዮጵያውያን እጣ ፈንታ በገንጣዮቹ እጅ እንዲወድቅ አደረገ፡፡ መንግስቱ ኃይለ ማርያም ለኢትዮጵያ አንድነት ‹‹አንድ ጥይትና አንድ ሰው›› እስኪቀር እንደሚዋጉ ቃል ገብተው እንደነበር ይነገራል፡፡ በእርግጥ እርሳቸው ብቻ ሳይሆን ሌሎችም መንግስቱ ኃይለማርያም ኢትዮጵያን ጦርነት ውስጥ ዘፍቀው መሸሸት እንደሌለባቸው በአደባባይ ነግረዋቸዋል፡፡ ለአብነት ያህል በመጨረሻው ሸንጎ አንድ የሀይማኖት መሪ መንግስቱ ኃይለማርያም አጣብቂኝ ውስጥ የከተቱትን ሀገርና ህዝብ ጥለው መሄድ እንደሌለባቸው በግልጽ እንዲህ ብለዋቸው ነበር፡፡ ‹‹….50 ሚሊዮን ህዝብ በጦርነት ባህር ማግደው፣ ቆስቁሰው፣ በእርስዎ ኃላፊነት 18 ዓመት ሙሉ መርተው ሳያደራድሩ፣ ሳያረጋጉ፣ የኢትዮጵያ ህዝብ ለእሳት ዳርገው፣ በአሁኑ ሰዓት ከመሞት በስተቀር፣ የቴዎድሮስን ጽዋ ከመጠጣት በስተቀር፣ ሌላ እድል የለዎትም፡፡ እንደሌሎች መሪዎች ኢሮፕ ይፈረጥ ጣሉ ብዬ እምነት የለኝም፡፡ እግዚያብሄር ምስክሬ ነው፡፡ ይህን ህዝብ አጋልጠው ይሄዳሉ አልልም፡፡ መንጌ፤ ከሷ ወንበር ላይ እንደቋንጣ ደርቀው እንደሚቀሩ አምንብዎ ታለሁ፡፡ ይህንን ባያደርጉ ግን ታሪክ ይፋረድዎታል፡፡››
በዚያ የሀይማኖት መሪዎች ስለ እውነት ይናገሩ በነበረው ወቅት ከንግግራቸው ሁለት የግንቦት ጦሶችን በግልጽ እንረዳለን፡፡ አንደኛውና ዋነኛው ፕሬዝደንት መንግስቱ የፈጠሩትን ቀውስ ‹‹….50 ሚሊዮን ህዝብ በጦርነት ባህር ማግደው፣ ቆስቁሰው፣ በእርስዎ ኃላፊነት 18 ዓመት ሙሉ መርተው ሳያደራድሩ፣ ሳያረጋጉ፣ የኢትዮጵያ ህዝብ ለእሳት ዳርገው፣›› ሲሉ ስለ ቀውሱ በግልጽ ተናግረዋል፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ ‹‹ይህን ህዝብ አጋልጠው ይሄዳሉ አልልም፡፡›› ሲሉ ህወሓትና ሻዕቢያ ለኢትዮጵያ ህዝብ ምን ያህል ጠላት እንደሆኑ በግልጽ የሚያሳይ ነው፡፡
meles zenawi
ግንቦት 13/1983 ከቀኑ 6 ሰዓት ላይ ‹‹ጓድ ሊቀመንበር››ን አሞካሽቶ የማይጠግበው ሚዲያ ‹‹ጦርነቱ ያስከተለውን ሁኔታ እንዲለወጥ በልዩ ልዩ ወገኖች በልዩ ልዩ መልክ ጥረት ሲደረግ ቆይቷል፡፡ ሆኖም ችግሩ አልተቃለለም፡፡ ስለዚህ ደም መፋሰስ እንዲቆም፣ ስምምነት እንዲሰፍን በልዩ ልዩ ወገኖች የሀገሪቱ ፕሬዝዳንት መንግስቱ ኃ/ማርያም ከስልጣን መውረዳቸው እንደሚበጅ የታመነበት ስለሆነ ይህንኑ በማመዛዘን ፕሬዝዳንት መንግስቱ ኃ/ማርያም በዛሬው ዕለት ከስልጣን ወርደው ከኢትዮጵያ ውጭ ሄደዋል፡፡ ፕሬዝዳንቱ ከስልጣን በመውረድ ሀገር ለቀው በመሄዳቸው የሪፐብሊኩ ም/ፕሬዘዳንት ሌፍትናንት ጀኔራል ተስፋዬ ወ/ኪዳን ተክተው ይሰራሉ፡፡›› ተባለ፡፡
‹‹ከመንግስቱ ኃይለማርያም አመራር ጋር ወደፊት!›› ይል የነበር ካድሬ ደግሞ ጆሮው ሊቀበለው የማይችለውን ነገር ሰማ፡፡ ለመንግስቱ ኃይለማርያም ቆሞ አመራሮቹን በጭካኔ ያረደው፣ በጭካኔ ዓይና ቸውን ያወጣውንና አስከሬናቸውን በአስመራ ጎዳና የጎተተው የ102ኛ ሰራዊት የመጨረሻው ተስፋውን ቆረጠ፡፡ ‹‹መንጌ!›› ሲል የነበረው የኢትዮጵያ ህዝብ እጣ ፈንታው ‹‹ገንጣይ አስገንጣይ›› ሲባሉና ኢትዮጵያን ሊገነጥሉ ሲታገሉ በኖሩት ሻዕቢያና ህወሓት ስር ሆነ፡፡ ሻዕቢያና ህወሓት በሚጠሏት ኢትዮጵያ ላይ የሚፈነጩበት መንገድ ወለል ብሎ ተከፈተ፡፡ ኢትዮጵያ በዚህ ጦሰኛ ግንቦት ወር አደጋ ውስጥ ገባች፡፡ ይባስ ብሎ ኮሎኔል መንግስቱ ኃይለማርያምን የተኩት ተስፋዬ ወልደኪዳን መንግስቱ ጥሎ ከወጣበት ከሁለት ቀን በኋላ የኢትዮጵያ ጦር መሳሪያውን ለ‹‹ወንበዴ›› አስረክቦ ወደ ፈለገበት ቦታ እንዲሄድ አዋጅ አስነገሩ፡፡ ለአንድነት ሲዋጋ የኖረው ሰራዊትም መሳሪያውን እየጣለ ወደየትውልድ ቦታውና ወደ ከተማው ሲያቀና ለህወሓትና ሻዕቢያ እንዲሁም በደርግ ለተማረረው አርሶ አደር ጥይት ሰለባ ሆነ፡፡ እንደ ምንም ብሎ ህይወቱን ያተረፈው ደግሞ በዚህ ደሙን ባፈሰሰላት አገር ጎዳና ላይ ወደቀ፡፡

ሰራዊቱ ትጥቁን እንዲፈታ በጊዜያዊ ፕሬዝደንቱ መጠየቁን ተከትሎ ሻዕቢያ በወቅቱ ሁለተኛዋ የኢትዮጵያ ከተማ የነበረችውን አስመራን ተቆጣጠረ፡፡ አረመኔዎቹ የሻዕቢያ ታጋዮች ኢትዮጵያውያንን እንደ ወራሪ ጠላት መዓት አወረዱባቸው፡፡ ህወሓት ኢህአዴግ ከአራት ቀን በኋላ ግንቦት 20 አዲስ አበባን ተቆጣጠረ፡፡ ደርግ መሸነፉን ተከትሎ ኢትዮጵያውያን ይህ ወር መልካም ነገር ይዞ ይመጣል ብለው ቢጠብቁም ያመጣው ግን ተቃራኒውን ሆነ፡

ግንቦት 20… ጥቁሩ ቀን

በግንቦት ወር የመጀመሪያ ቀናት ሻዕቢያና ህወሓት አሜ ሪካን ጨምሮ ከምዕራባውያን መንግስታት ጋር ሎንደን ውይይት አድርገው ነበር፡፡ ከዚህ ውይይት ዋና ጭብጥ መካከል አንዱ ኢትዮጵያ የባህር በር ያስፈልጋታል በሚል ከምዕራባዊያኑ በተለይም ከአሜሪካ የተነሳው ሀሳብ ነበር፡፡ ይሁንና መለስ ዜናዊ ኢትዮጵያ የባህር በር እንደማያስፈልጋት ሽንጡን ገትሮ በመከራከር ምን አል ባትም ‹‹ለማስተዳደር›› በሚፈልጋት አገር ሉዓላዊነትን አሳልፎ የሰጠ የመጀመሪያው መሪ የሚያደርገውን ከሃዲነት ፈጸመ፡፡ ግንቦት 21 ቀን ኤርትራ በሻዕቢያ ስር መተዳ ደር ጀመረች፡፡ ያ የተደከመበት፣ በርካታ የሰው ነፍስ የጠፋበት ሉዓላዊነት ግብጽ ጀምራው እነ ሶማሊያ፣ ሱዳንና ሌሎች የአረብ አገራት ትኩስ ስንቅ እየቋጠሩላቸውና የደርግም ስህተት ተጨምሮበት በአገር አንድነት ላይ በተ ነሱት ‹‹ወንበዴዎች›› የበላይነት ተጠናቀቀ፡፡ ሉዓላዊነቷ ተደፈረ፡፡

ህወሓትና ሻዕቢያ ስልጣን ከመያዛቸው በፊትም ጀምረው ተሻርከው እንጨት፣ ብረት፣ ቡና፣ ወርቅ፣ ብር፣ ሳይሉ ያገኙትን የኢትዮጵያን ሀብትና ንብረት መዘበሩ፡፡ ከደርግ ጋርም ሆነ ካለፉት ስርዓት ጋር ግን ኙነት አለው ያሉትን ህዝብ ላይ እስራት፣ ግድያና ሌሎች አሰቃቂ እርምጃዎችን ወሰዱ፡፡ እርግጥ ነው ይህ ተባብሮ ኢትዮጵያን የመመዝበር ተግባር በስምምነት አልዘለ ቀም፡፡ ሁለቱ የኢትዮጵያን ምጣኔ ሃብት ለማጋበስ በመ ነበራቸው አለመግባባት እርስ በእርስ መነካከስ ጀመሩ፡ ፡ በዚህ የሁለት ጅቦች ጠብ ምክንያትም ህወሓት የሚ ገዛት ኢትዮጵያ ግንቦት 4/1990 ዓ.ም በሻዕቢያ ተወረ ረች፡፡ በሁለቱ ግለሰቦች፣ ፓርቲዎች ኢኮኖሚያዊና ድሮ ኢትዮጵያን ለመገነጣጠል በርሃ በነበሩበት ወቅት በተፈ ጠረ ቁርሾ 70 ሺ ያህል ህዝብ በዚህ ወርሃ ግንቦት በተፈ ጠረ ግጭት ሰበብ ውድ ህይወቱን አጣ፡፡ በዚህ ግጭት ምክንያት በርካታ ኢትዮጵያውያን ጥርሳቸው ሳይቀር እየ ተነቀለ ከአስመራ ተባረሩ፡፡ ህወሓት/ኢህአዴግም ቢሆን ያ አብዛኛውን ተግባሩን ካስተማረው ሻዕቢያ በቀሰመው ተሞክሮ መሰረት ምላሹን ሰጠ፡፡
ህወሓት/ኢህአዴግ ስልጣን ከያዘ በኋላ እርዳታ ለመ ለመን እከተለዋለሁ ካለው የይስሙላ ዴሞክራሲ ስም አፋኝነቱን ያሰፈነ ድርጅት ነው፡፡ ከኢትዮጵያ ጥቅም ይልቅ የራሱንና የሻዕቢያ ጥቅም አስቀድሟል፡፡ ኢትዮጵ ያውያንን በዘውግ ከፋፍሎ መግዛትን እንደዋነኛ ስልት ወስዶታል፡፡ የይስሙላህ ዴሞክራሲና ምርጫ አሰፈንኩ ቢልም ከመግዢያነት ያለፈ ግን አልነበረም፡፡ ለዚህም ህወሓት/ኢህአዴግ ስቃይ እያደረሰበት የሚገኘውን ህዝብ ጥላ ለመሆን በህገ መንግስቱ መሰረት የተቋቋሙት ፓርቲዎችና ፖለቲከኞቻቸው የደረሰባቸውን መከራ ማንሳት በቂ ነው፡፡ ለምሳሌ ያህል በየክልሉ ኦነግና ህወሓት/ኢህአዴግ ሲጨፈጭፉት የነበረውን ኢትዮጵያ ዊና የኢትዮጵያ አንድነት ለመታደግ የተነሳው መዐሕድ የመጀመሪያው ተጠቂ ነበር፡፡ የዚህ ፓርቲ መስራችና
እውቁ ፕሮፌሰር አስራት ወልደየስ ደግሞ የዚህ የግንቦት ዘራሽ አምባገነን ስርዓት ዋነኛ ተጠቂ ናቸው፡፡ ፕሮፌሰሩ እስር ቤት ሲማቅቁ ቆይተው ግንቦት 1/1991 ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል፡፡ የሚገርመው መንግስቱ ኃይለማርያም እና ውጫዊ የኢትዮጵያ ጠላቶች በከፈቱላ ቸው ቀዳዳ በግንቦት ነፋስ ወደ ስልጣን ብቅ ያሉትና የአሁኑ ስርዓት ‹‹መሃንዲስ›› መለስ ዜናዊም በዚሁ የደም ወር እውቁ ፕሮፌሰር ተሰቃይተው በሞቱበት ቀን የተወ ለዱ መሆናቸው ነው፡፡ ፕሮፈሰሩ ከሞቱ በኋላ የመዐሕድ አካል የነበሩም ሆነ ሌሎች የፖለቲካ ኃይሎች በ1997 ተጠናክረው በአዲስ ምዕራፍ ለትግል የመጡበት ዘመን ነበር፡፡ በተለይ የግ ንቦት 1997 ምርጫ ኢትዮጵያውያን ካሉበት አምባገነ ናዊ አገዛዝ ነጻ እንዲሚያወጣ በኢትዮጵያውያኑ ብቻ ሳይሆን ህወሓት/ኢህአዴግ ለኢትዮጵያ፣ ለቀጠናውና ለዓለምም እንደማይመጥንና እንደማይበጅ በተረዳው ዓለም አቀፍ ማህበረሰብ ዘንድ ተስፋ ተጥሎበት ነበር፡፡ ኢትዮጵያውያን በታሪካቸው ለመጀመሪያ ጊዜ በምርጫ ነጻ ለመውጣት በሙሉ ልብ ወደ ምርጫ ጣቢያ የጎረፉ ትም በዚህ ቀን ነው፡፡ የሚያዝያው ሰልፍና ሌሎች መነ ቃቂያዎች ግንቦት 7 ኢትዮጵያውያንን ነጻ የምታወጣ ቀን አስመስሏታል፡፡ እነዚያ ንፍሮ ቀቅለው፣ ቡና አፍል ተው ግንቦት ክፉውን ይዞ እንዳይመጣ ተስፋ ሳይቆረጡ ሲልምኑ የኖሩት ኢትዮጵያውያን አሁን አዲስ ተስፋ ሰንቀዋል፡፡ ተስፋው ከአንድ ቀን በላይ አልዘለለም እንጂ፡፡

ተቃዋሚ አጣን ሲሉ የነበሩት አቶ መለስ ዜናዊ ማታ ላይ ብቅ ብለው ይህን የግንቦት 7 ተስፋ አቧራ ነሰነሱበት፡፡ ማታ በኢቲቪ ብቅ ብለው አሁንም ድረስ ኢትዮጵያውያንን ለቀየደው የጸረ ሽብር፣ የሲቪክ ማህበራት፣ የሚዲያ…..ሌሎች ቀያጅ አዋጆች መሰረት የሆነውን ጊዜያዊ አዋጅ አወጁ፡፡ በነጋታው ግንቦት 8/1997 ህዝብ ከቤት ውጭ ምንም አይነት ስብሰባም ሆነ እንቅስቃሴ እንዳያደርግ ተከለከለ፡፡ በዚሁ ቀን ‹‹አብዮታዊ›› ፓርቲው ምርጫ ቦርድ ምንም ባላሳወቀበት ግንቦት 8 ከአዲስ አበባ ውጭ በሌሎች የአገሪቱ ክፍሎች ማሻነፉን በተቆጣጠረው ሚዲያ አሳወቀ፡፡ ከዚህ ጊዜ ጀምሮ የሰላማዊ ትግልን የቀፈደዱ በርካታ እርምጃዎች በዚሁና በቀጣዩ ግንቦቶች ተወስደዋል፡፡ ግንቦት 2002 ዓ.ም ምርጫ ደግሞ አፋኝነቱን ያጠናከረው ኢህአዴግ አስፈራርቶም፣ አጭበርብሮም 99.6 በመቶ አሸንፎ ‹‹አውራ ነኝ›› ያለበትን ኢትዮጵያውያንን በገዥነት እንደሚቀጥል ያቀደበት ወቅት ሆነ፡፡ ባለፉት 5 አመታት ፖለቲከኞችን፣ ጋዜጠኞችን፣ ፖለቲካውን ያነቃቃሉ ብሎ የፈራቸውን ብሎገሮች አስሮ፣ ህዝቡን 1ለ5 ጠርንፎ፣ እና አጭበርብሮ የዘንድሮውን ምርጫ 100 በ100 እንዳሸነፈ እየተነገረ ነው፡፡ በእርግጥ በተለይ ከ1997 በኋላ አብዛኛዎቹ ኢትዮጵያውያን ኢህአዴግ የሚወዳደሩት ሳይሆን የሚታገሉት እንደሆነ በማመናቸው ምርጫውን 90፣99.6፣ 100 አሸነፍኩ ቢል የሚገርማቸው አይደለም፡፡ ያም ሆኖ ግን ግንቦት ለኢትዮጵያውያን የመከራ ወር እንደሆነ ቀጥሏል፡፡

በአጠቃላይ ግንቦት 20 ህወሓት/ኢህአዴግ ሳይገባው፣ ለኢትዮጵያውያን ሳያስብና ኢትዮጵያዊ ሳይሆን ኢት ዮጵያን የተቆጣጠረበት፣ በኢትዮጵያውያን ላይ ፕ/ር መስፍን እንደሚሉት ‹‹ህገ አራዊት›› መተግበር የጀመረበት፣ ዓለም አንድ በሆነችበት ወቅት መገንጠልን በወርቃማ መብትነት ያጸደቀበት፣ ኢትዮጵያውያን አገራ ቸው ውስጥ እንዳይዘዋወሩ የማንነት ግንብ የገነባበት ጥቁር ቀን ነው፡፡ በተለይ ከኢትዮጵያዊ አላማ ያፈነገጠ መሆኑ፣ ኢትዮጵያው ያንን በስስ ማንነት መከፋፈሉ፣ ለራሱ ቡድናዊ ጥቅም መሯሯጡ ህወሓት/ ኢህአዴግ አዲስ አበባን የተቆጣጠረበትን ቀን ለኢትዮጵያውያን ጨለማ፣ አዲስ የጭቆና ዘመን ነው፡፡ ይህን ቀን ምናልባትም የጀርመኑ ሂትለር ለቤልጀም ሳይሆን ለራሱ የስልጣንና ልሂቃን ጥቅም፣ በበላይነት ተወጥሮ ቤልጀምን ከወረረበት የሁለተኛው የዓለም ጦርነት ግንቦት 1940 ተመሳሳይ ወቅት (ግንቦት 20) ጋር ማመሳሰል ይቻላል፡፡ እንዲያውም ናዚዎቹ የጀርመንን ጥቅም ለማስጠበቅ፣ ቤልጀምን ሰጥ ለጥ አድርገው ለመግዛት ግልጽ አላማ ይዘው ነው የገቡት፡፡ ህወሓት ግን እስካሁንም ድረስ፣ ለባለፉት 23 አመታት የሚጠላትን አገር የገንጣይ ስምና አላማውን እንዳነገበ እየገዛት ይገኛል፡፡ አሁንም ድረስ ኢትዮጵያውያን ንፍሮ አንፍረው፣ ቡና አፍልተው ‹መከረኛውን› አምላካ ቸውን መለመናቸው ቀጥለዋል፡፡ ግንቦት የሰጠው ‹‹አብ ዮታዊ›› ፓርቲ ግን በከፍፍለህ ግዛ፣ በስራትና ግርፋት፣ በኑሮ ውድነት፣ በመሰረታዊ አገልግሎት እጥረት፣ በሙስና ኢትዮጵያን የመከራ ምድር አድርጓታል፡፡ ግንቦት ደግሞ በአየር ንብረት ብቻ ሳይሆን በፖለቲካ ውም ውጥንቅጡ የወጣ ክፉ ወር ሆኖ ቀጥሏል፡፡ ይህም ነው ግንቦት አሁንም የህወሓት/ኢህአዴግ እንጂ የኢት ዮጵያውያን ወር አይደለም ለማለት የሚያስደፍረው፡፡

(ይህ ጽሁፍ ከመጠነኛ ማስተካከያ ውጭ ግንቦት 15/2006 ዓ.ም ነገረ ኢትዮጵያ ላይ የወጣ ነው)

The post ግንቦትና ግንቦታውያን appeared first on Zehabesha Amharic.

↧
Viewing all 15006 articles
Browse latest View live


<script src="https://jsc.adskeeper.com/r/s/rssing.com.1596347.js" async> </script>
<script src="https://jsc.adskeeper.com/r/s/rssing.com.1596344.js" async> </script>