Quantcast
Channel: Ethiopian News | ዘ-ሐበሻ | Latest News Provider | News For All
Viewing all 15006 articles
Browse latest View live

ለኢትዮጵያና ለአፍሪካ ቀንድ ነጻነት፥ ሰብአዊ መብትና፥ ዲሞክራሲ ወሳኝ ግብዓቶች ናቸዉ።

0
0

ግንቦት 10 ፤ 2007

Ethiopia-and-the-Horn-628x319የኢትዮጵያ ሳተላይትና ሬዲዮ ድርጅት (ኢሳት) ከምሁራንና ከሌሎች ወሳኝ አካላት ጋር በመተባበር ከግንቦት 1-2 2007 ዓ.ም. ኢትዮጵያና ምስራቅ አፍሪካ: ለዲሞክራሲ ለሰላምና ለብልጽግና የወደፊት አቅጣጫ” በሚል ርዕስ ያዘጋጀዉን የሁለት ቀን ሲምፖዝየም እጅግ በተሳካ ሁኔታ አጠናቋል። ስብሰባዉ የተለያዩ የማህበረሰብ አካላት፥ ባህሎችና፥ አመለካከቶች የተስተናገዱበት ከመሆኑን በላይ የአፍሪካ ቀንድ አሁን ያለበትን ጆግራፊያዊ፥ ሃይማኖታዊ፥ ባህላዊ፥ ኢኮኖሚያዊ ግንኙነቶችና ፍልሰቶችን ትክክለኛ ገፅታ ግንዛቤ ዉስጥ በማስገባት እጅግ የተሳሰረ መሆኑን አሳይቷል። ታሪካችን አብሮነትን ያንጸባርቃል።

ይህ በትክክለኛ ወቅት ላይ የተካሄደዉ ሲምፖዝየም ያተኮረባቸዉ ዋና ዋና ነጥቦች

  1. በሰብአዊ መብት፥ በአስተዳደር፥ በሲቢል ማህበረሰብ፥ በዘዉግ አስተሳሰብ፥ በማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮች፥ በጅምላ ስደት፥ በሙስና፥ በህገወጥ የገንዘብ ሸሽት እና ዝዉዉር
  2. በ2007 የኢትዮጵያ ፓርላማ ምርጫ ገፅታ
  3. በአዲስ ፖሊሲ ቀረፃና የወደፊት አቅጣጫ የአመለካከት ለዉጥ
  4. በወደፊት እቅድና አቅጣጫ ላይ አጠቃላይ መግለጫ

የስብሰባዉ ተሳታፊዎች በመፈራረስ ላይ ያሉ ወይም የመፈራረስ አደጋ የተጋረጠባቸዉ አገሮች ላይ የሚታዩ፥ ሆን ተብለዉ ህዝባዊ አመጽ ሊፈጥሩ በሚችሉ፥ የመገንጠል አደጋ በሚያመጡ፥ አለመረጋጋትን እና አሸባሪነትን በሚያስፋፉ የግጭት ምክንያቶችንና መንስኤዎችን ላይ በዝርዝር ትንተናና ክርክር አድርገዉባቸዋል። ኢትዮጵያ በመልካም ጎኗ ለአጠቃላይ አፍሪካ ቀንድ ብሎም ለምስራቅ አፍሪካ በፖለቲካና በስትራቴጂ እጅግ ጠቃሚ አገር መሆኗን የስብሰባዉ ተሳታፊዎች ተስማምተዋል። እምቅ የተፈጥሮ ሃይሏ፥ ከሰዉ ሃብቷና እ.ኤ.አ. በ2014 ካገኘችዉ 4 ቢሊዮን ዶላር በላይ የዉጭ እርዳታ ጋር ተዳምሮ አካባቢዉን በማረጋጋት እና መስመር በማስያዝ በኩል ክፍተኛ ጠቅሜታ ቢኖራትም፥ በአንድ ፓርቲ የበላይነት የምትተዳደር፥ ሃይማኖታዊና የዘዉግ ቁርቋሶ የሚስተናገዱባት፥ ሃብቶቿ በሙስና የሚባክኑባት፥ የፖአቲካና ማህበራዊ መጫወቻ ሜዳዎቿ ተጠርቅሞ የዘጋባት፤ መሰረታዊ የነጻነትና ሰብአዊ መብቶቿ ያልተከበረባት፥ የህግ የበላይነት የሚጣስባት፥ እዉነተኛ መድበለ ፖለቲካ የተከለከለባት አገር በመሆኗ፥ የነበራት አቅም፥ ተሰሚነትና ሃይሏ ቀስ በቀስ እያሽቆለቆለና እየተሸረሸረ መጥቷል።

 

የሲምፖዚየሙ ተሳታፊዎች ከ1983 ዓ.ም. በፊት ጀምሮ በጉልበት ስልጣን ላይ የተቆናጠጠዉ የኢትዮጵያ ህዝቦች አብዮታዊ ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ (ኢህአዴግ) ህዝቡን ለማስተዳደር ብቃት እንደሌለዉና ተአማኒነትና እንዳጣ በሙሉ ድምፅ ተስማምተዋል። ኢህአዴግ ህዝቦችን የሚያቃቅሩ ማለትም ፍርሃት፥ ግብታዊነት፥ ሽብርተኝነት፥ የእርስ በእርስ ሽኩቻ የመሳሰሉ እኩይ ሁኔታዎችን በመፍጠር አገሪቷን አደጋ ላይ ከመጣሉም ባሻገር፤ ለሉአላዊነቷም ከፍተኛ አደጋ ሆኖ ተጋርጧል። እነዚህም ችግሮች አብዛኞቹ ወጣቶች በሚሆኑ በመቶ ሚሊዮን ኢትዮጵያዉያን ህይወት ላይ አስነዋሪ ጥላ ሊጥሉ የሚችሉ ናቸዉ። የሰብአዊ መብቶች ድርጅት (Human Rights Watch) በርዕሰ-አንቀጹ “ምርጫዎች፤ የኢትዮጵያ ተምሳሌትነት” በሚል ርዕስ እንዳሰፈረዉ “ካለፈዉ ምርጫ ጀምሮ ገዢዉ ፓርቲ የመሰብሰብና የንግግር መብቶች ላይ ከፍተኛ ቁጥጥር እና አፈና አድርጓል።” ገዢዉ ፓርቲ ተቃዋሚዎችንና ተፎካካሪዎችን በተፈበረከ ዉሸት በሽብርተኝነት ይከሳል፥ ይደበደባል፥ ያስራል፥ ወይም አገር ጥለዉ እንዲሰደዱ ያደርጋል። ኢህአዴግ እ.ኤ.አ. በ2014 ብቻ ከሰላሳ በላይ ጋዜጠኞች አገር ጥለዉ እንዲወጡ አድርጓል፤ በቁጥር ያልተገለጹ ተቃዋሚዎችን በማሰር ያለፍትህ እንዲማቅቁ አድርጓል። የፍትህ ስርዓቱ የፖለቲካ ወገንተኝነት ሌላዉ እራስ ምታት ነዉ። እ.ኤ.አ. በ2009 የወጣዉ ፀረአክራሪነት ህግና የመያዶ ድርጅቶችን አዋጅ የሲቢል ማህበራት በመንግስት ላይ ተቃዉሞ ሊያሰሙ በሚችሉ ድርጅቶች ላይ የተቃጣ ስለት ሆኗል።

ሲምፖዚያሙ በቅርቡ የሚደረገዉ ምርጫ ካለፉት ምርጫዎች የተለየ እንዳልሆነና፤ የሰብአዊ መብቶች ድርጅት (Human Rights Watch) እንዳለዉ በግንቦት 2007 ዓ.ም. ምርጫ የተቃዋሚ ፓርቲዎች በነጻነትና በአግባቡ መንቀሳቀስ እጅግ ከባድ ፈተና ሆኖባቸዋል። አንድ ኢትዮጵያዊ አክቲቪስት፥ በኢትዮጵያ ዉስጥ ያለዉን አስፈሪ ድባብ እና ጭቆናን አስመልክቶ ለሰብአዊ መብቶች ድርጅት “ባደባባይ ሰልፍ ብንወጣ እንታሰራለን፤ ስለፖሊሲ መቀየር ቢሮያቸዉ ሄደን ብንጠይቅ “አሸባሪ” እንባላለን፥ በፍርድ ቤት ብንከስ ነጻነት የለንም፤ ዘብጥያ እንወርዳለን። ስለዚህ ምን ማድረግ ይሻለናል?” ሲል ምሬቱን ገልጿል። ዘጋርዲያን የተባለዉ ጋዜጣ “ኦርዌሊያን” ብሎ በሰየመዉ አይነት ኢትዮጵያ በአንድ ፓርቲ ቁጥጥር በጭካኔ የምትመራ አገር ሆናለች። የኢትዮጵያ መንግስት በየአመቱ በመቶ ሚሊዮኖች የሚቆጠር ገንዘብ አንድ ለአምስት (1፡5) ለተባለ የአፈና አደረጃጀትና ለስለላ መዋቅሩ ያባክናል። አንድ ለአምስት የተባለዉ የአፈና አደረጃጀት፥ አንድ ሰዉ የሌሎችን 5 ሰዎች ውሎ (ሰዎቹ ከሌሎች ሰዎች ጋር ያላቸዉን ግንኙነት፤ ህብረትና፥ እንቅስቃሴ) ቀን በቀን እየተከታተለ ለበላይ ሃላፊዎች ሪፖርት የሚያደርግበት መዋቅር ነዉ። የገዢዉ ፓርቲ ጠላት ተብሎ የተፈረጀ ወይም የተጠረጠረ ግለሰብ ያለፍርድ ቤት ትዕዛዝ ይታሰራል፥ ይደበደባል፥ ይንገላታል። ስልክ ኢንተርኔት ማህበራዊ ሚዲያ ከፍተኛ ቁጥጥር ይደረግባቸዋል፤ ከኢትዮጵያ ዉጭ የየትኛዉም ሚዲያ በአገር ዉስጥ እንዲሰራጭ አይፈቀድም። አፈናዉ መበርታት ለአመጽና ለሽብርተኝነት በር ይከፍታል።

ሲምፖዚየሙ ሂዉማን ራይትስ ዎች በቅርቡ በኢትዮጵያ ፓርላሜንታዊ ምርጫ ላይ ያቀረበዉን ግምገማ እጅጉን ያደንቃል። በቅርቡ የአሜሪካ የዉጭ ጉዳይ ሚኒስትር የፖለቲካ ጉዳዮች የበታች ሃላፊ የሆኑት ዊንዲ ሸርማን “ኢትዮጵያ ዲሞክራሲያዊ አገር ናት። የሚቀጥለዉ ምርጫ ነጻ፥ ፍትሃዊ፥ ታማኝ፥ ግልፅና፥ አሳታፊ ይሆናል” የሚል የተሳሳተ አስተያየት ሰጥተዉ ነበር። ሂዉማን ራይትስ ዎች ከዋሽንግተን ፖስት ጋር ተቀራራቢ የሆነ ርዕሰ አንቀጽ እ.ኤ.አ. በግንቦት 1 2015 “ማስመሰል እንደኢትዮጵያ” በሚለዉ ሓተታዉ “በኢትዮጵያ ዉስጥ የሚደረገዉ ጭቆና ዋሽንግተ ማዉገዝ እንጂ ማድነቅ አይገባትም” በማለት የሃላፊዋን አስተያየት ኮንኗል። ፍሪደም ሃዉስ፥ ሂዉማን ራይትስ ዎች፥ አምነስቲ ኢንተርናሽናል፥ የኢትዮጵያ የሰብአዊ መብቶች ፕሮጄክት፥ የጋዜጠኞች ተከላካይ ድርጅት፥ ኢንተርናሽናል ሪቨርስ እና ኢትዮጵያዉያን ዊንዲ ሸርማን ንግግራቸዉን እንዲያስተባብሉ ለአሜሪካ የዉጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጆን ኬሪ የተቃዉሞ ደብዳቤ ፅፈዋል። የሲምፖዚየሙ ተሳታፊዎች ከላይ ከተገለጸዉ ርዕሰ አንቀጽ ጋር በመስማማት ኢትዮጵያ ዲሞክራሲያዊ አገር ለመሆኗ ምንም በመረጃ የተደገፈ ነገር አለመኖሩን አስምረዉበታል። በተቃራኒዉ የኢትዮጵያ መንግስት ተስፋ የሚያስቆርጥና ፍርሃት የነገሰበት አፋኝ ስርዓትን በመፍጠር በቋፍ ላይ ያለችዉን አገር ወደባሰ አዘቅት ዉስጥ እየገፋት ይገኛል። በኢትዮጵያ ዉስጥ ሰፍኗል የተባለዉ የዉሸት ሰላምና መረጋጋት በጉልበትና በአፈና ላይ የተመሰረተ ነዉ።

ይሁን እንጂ የአንድ አገር አለመረጋጋት ወደመበታተን ሊመራ እንደሚችል የሲምፖዚየሙ ተሳታፊዎች ያምናሉ። ጭቆናዉና አፈናዉም ወደማያባራ የእርስ በእርስ ህዝባዊ አመጽና ጦርነት ሊሸጋገር ይችላል። ይህ ድርጊት ሊቆም የሚችለዉም የምራባዊያን ዲሞክራሲያዊ አገራት በተለይም አሜሪካ የኢትዮጵያ መንግስት የዲሞክራሲ እሴቶችንና፥ የህግ የበላይነትን እንዲያከብር የተፅእኖ ሃይላቸዉን ማሳረፍ ሲችሉ ብቻ ነዉ። ኢትዮጵያ እና ኢትዮጵያዉን ከገጠማቸዉ አስከፊ ሁኔታዎች አንጻር ሲምፖዚየሙ የሚቀጥሉትን ዉሳኔዎች በማስተላልፍ የመትሄ ሃሳቦችን አስቀምጧል።

  • ክርስቲያ ወንድሞቻችን በአይኤስ በግፍ መታረዳቸዉን፥ ህግ አክባሪ ኢትዮጵያዉያን በደቡብ አፍሪካ መገደላቸዉን፥ በየመን ኢትዮጵያዉናንና ሌሎች በአየር የመደብደባቸዉን ድርጊት እናወግዛለን፤ የኢትዮጵያን መንግስትም ህዝብን ያማከለ አሳታፊና ተጠቃሚ የሚያደርግ የስራ ፈጠራ እድገት መርሃ ግብር እንዲያወጣ እንጠይቃለን።
  • በኢትዮጵያ ያሉ ሁሉም ተቃዋሚዎች፥ የሲቪል፥ ፕሮፌሽናልና የሃይማኖት ድርጅቶች፥ የሰብአዊ መብት ተከራካሪ ቡድኖች፥ አክቲቪስቶችና ምሁራን አንድነትን በብዘሃነት መነጽር እንዲያዩትና እንዲደግፉ፥ ለአንድ አላማ አብሮ ለመስራት ቆርጠዉ እንዲነሱና አማራጭ ሃሳቦች የሚንሸራሸሩባት፥ ዲሞክራሲያዊነት የጎለበተባት፥ ሁሉን አቀፍ የሆነች ኢትዮጵያን ለመፍጠር እንዲረባረቡ እንጠይቃለን።
  • ሁላችንም የተገነዘብነዉ ነገር የኢትዮጵያ ህዝብ፥ አፍሪካ ቀንድና የምራባዉያን አገሮች በዘላቂነት የሰብአዊ መብት እንዲከበር፥ ነጻነት እንዲኖር፥ ተጠያቂነትና አሳታፊነት እንዲጎለብት ይፈልጋሉ፤ ለዚህም ይታገላሉ። በመሆኑም የአሜሪካ መንግስት ትርጉም ያለዉ ለዉጥ ለማምጣት በኢትዮጵያ ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ በማሳደር የፖለቲካ ምህዳር እንዲሰፋ፥ ብሄራዊ እርቅ እንዲደረግና፥ ሁሉም አካላት የስልጣን ተካፋይ እንዲሆኑ በማመቻቸት ችግሮቹ ከመባባሳቸዉ በፊት አወያይቶ ሊፈታ ይገባል።
  • የአሜሪካ መንግስትን በኢትዮጵያ መንግስት ላይ የሚያወጣቸው የማስመሰል መግለጫዎችና የተለሳለሱ አቋሞች ወይም አቀራረቦች እንደማይሰሩ እንዲረዳልን እንፈልጋለን። አሜሪካ ሚዲያን፥ ፖለቲካ ፓርቲዎችንና ተቃዋሚዎችን ለሚያፍነዉ መንግስት ትርጉም ያለዉ ለዉጥ እስካልመጣ ድረስ ድጋፏን እንድታቆም እንጠይቃለን።
  • አለም አቀፍ ማህበረሰብ አባላት በተለይም ምዕራባውያን ለጋሽ አገራት፥ መንግስታትና የዉጭ ኢንቨስተሮች ኢትዮጵያ ሚሊዮኖችን ከስራ ዉጭ ያደረገች፥ ኢፍትሃዊነት እንዲነግስባት የተደረገች፥ ሁሉንም ቡድኖች ያላማከለ የአስተዳደር ችግር ያለባት አገር መሆኗን እንዲገነዘቡ እንፈልጋለን። በቅርቡ በአይስ (ISIS) የተደረገዉ የጅምላ ግድያ ኢትዮጵያ ዉስጥ አለ የተባለዉ እድገት የተጣመመ ለመሆኑ አመላካች ነዉ። ኢትዮጵያዉያን ወጣቶች በዉጭ አገር ስራ ለማግኘት ሲሉ ህይወታቸዉን ለአደጋ በመስጠት ለህገወጥ የሰዉ አዘዋዋሪዎች ገንዘብ ይከፍላሉ። የኢትዮጵያ መንግስት ወደ 400 ገደማ የሚጠጉ በሚሊዮን የሚቆጠር ገንዘብ የሚያጋብሱ የህገወጥ ሰዉ አዘዋዋሪ ደላሎችንና ድርጅቶችን እንዲዘጋና የወጣቶች የስራ ፈጠራ ፕሮግራሞችን በአስቸኳይ እንዲነድፍ እንጠይቃለን።
  • የኢትዮጵያ መንግስት ሁሉንም የፖለቲካ እስረኞች ያለምንም ቅድመሁኔታ በአስቸኳይ እንዲፈታ፤ የፀረሽብርተኝነትና የመያዶ ህጎችን እንዲሽራቸዉ እንጠይቃለን።
  • የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስደተኞች ከፍተኛ ኮሚሽነር፥ የቀይ መስቀልና የቀይ ጨረቃ ማህበራት ወደኢትዮጵያ ቢመለሱ ችግር ለሚደርስባቸው በሊቢያና በየመን ዉስጥ በችግር ለሚሰቃዩ የኢትዮጵያ ስደተኛ ወገኖች ከለላ እንዲሰጣቸዉ በአሜሪካና በሌሎች አገሮች ጥገኝነት እንዲያገኙ እንዲያመቻችላቸዉ ስንል እንጠይቃለን። የምራባዉያን መንግስታት፥ ጃፓን እና ሃብታም አገሮች ለኢንተርናሽናል ኦርጋናይዜሽን ፎር ማይግሬሽንና (IOM) ለሌሎች ድርጅቶች ለስደተኞች ግልጋሎት የሚዉል ገንዘብ እንዲለግሱ እንጠይቃለን።
  • የአሜሪካ የኮንግሬስ አባላት የሰብአዊ መብት ጥበቃ፥ የህግ የበላይነትና ዲሞክራሲን ያግዛል የተባለለትን የ2007 የዲሞክራሲና ተጠያቂነት ረቂቅ ህግ እንደገና እንዲያንሸራሽር በጥብቅ እንጠይቃለን። ኢትዮጵያዉያን ነጻነት፥ ክብር፥ የሰብአዊ መብት ከለላ እና ዲሞክራሲያዊ መብቶች ከመቼዉም ጊዜ በላይ እንደሚያስፈልጋቸዉ እናምናለን።

 

የስብሰባዉ አዘጋጅ ኮሚቴ የተሰብሳቢዎቹን ቀልብ የሳቡ ርዕሶችን በጊዜ እጥረት ምክንያት በበቂ ሁኔታ ሳያወያይባቸዉና ሳይሸፍናቸዉ ቀርቷል። ለወደፊቱ ግን በእነዚህ ርእሶች ላይ በጥልቀት እንድወያይ መድረኮችን ያመቻቻል።  ከርዕሶቹ በጥቂቱ

  1. የኢትዮ ኤርትራ ግንኙነት
  2. ዕርቅና ሰላም በአፍሪካ ቀንድ
  3. አዲሱ ሚዲያ (ፌስቡክ፥ ትዊተር፥ ዩቲዩብ፥ ወዘተ) በመንግስት፥ በዲሞክራሲ፥ እና በሰብአዊ መብት ግንዛቤ ዙሪያ ላይ ላይ ያለዉ ሚና
  4. ተቀራራቢነት ያላቸዉ ሌሎች ሃሳቦችም ይስተናገዳሉ።

 

Contact information:

 

ጥያቄ ካለዎት  ኢሜይል ethio-horn@ethsat.com ሊያገኙን ይችላሉ። በስልክም እንዲሁ በ571- 335-4964 ይደዉሉልን።

 

The post ለኢትዮጵያና ለአፍሪካ ቀንድ ነጻነት፥ ሰብአዊ መብትና፥ ዲሞክራሲ ወሳኝ ግብዓቶች ናቸዉ። appeared first on Zehabesha Amharic.


ድምጻዊት ራሔል ዮሐንስ

0
0

አንጋፋዋ ድምፃዊ ራሔል ዮሐንስን በሃበሻ ልብስ ደምቃና አምራ ነበር ያገኘኋት- ባለፈው ረቡዕ ምሽት፡፡ በተንጣለለው ግቢዋ ጋራዥ ቤት ውስጥ ሽንጣም ኒሳን መኪናዋ ቆሟል:: ግራውንድ ፕላስ ዋን መኖርያ ቤቷ በአካባቢው ካሉ መኖሪያቤቶች እጅግ ማራኪና ትኩረት የሚስብ ነው፡፡ ሳሎን ቤት ስገባ ትልቅ ድግስ የተዘጋጀ ይመስል ነበር፡፡ ጥሬ ስጋው ጠጁ፣ ጠላው ተደርድሮ ነው የደረስኩት፡፡ ራሔል እንደነገረችኝ ማክሰኞ ዕለት ቤቷ ማህበር ነበር፡፡ የስድስት ልጆች እናት ብትሆንም አሁን ልጆችዋ አብረዋት የሉም – በአሜሪካና በካናዳ ነው የሚኖሩት፡፡ እሷ ከዘመድ ልጆች ጋር ትኖራለች፡፡ በ1970ዎቹ መጀመሪያ ላይ ወደሙዚቃ ሙያ ከገባችው ራሔል ዮሐንስ ጋር በህይወቷና በሙያዋ ዙሪያ ያላወጋነው ነገር የለም፡፡ በቤተመንግስት አጉራሽ እንደነበረች፣ በጊዮንና በሂልተን ሆቴል በዋይን ገርልነት መሥራቷን፣ አንዳንዴ ዘፈኗን በእንግሊዝኛ እንደኮሜዲ ታቀርብ እንደነበረ ወዘተ— ነግራኛለች፡፡ ከጓደኞቿ ጋር ስላላት ማህበር እንድትነግረኝ በመጠየቅ ነው ወደ ጭውውታችንን የገባነው፡፡
ድምጻዊት ራሔል ዮሐንስ
ማህበሩ የጓደኞች ነው የቤተሰብ?

የት/ቤት ጓደኞቼም የቤተሰብም አለኝ፡፡ ከ40 ዓመት በፊት የተጀመረ ነው፡፡ አንዳንድ ጓደኞቼ፣ እህቶቼ ቢያልፉም እስከዛሬ ይሄው ማህበሩን እንጠጣለን፡፡ ዛሬ አንቺም ወደ ቤቴ የመጣሽው የመድሃኒያለም ማህበር ትናንት አውጥቼ ነው፡፡ በጣም የተለየ ፍቅር አለን፡፡
የትምህርት ቤት ጓደኞችሽ—የት ነው የተማርሽው?
የቄስ ትምህርት አባታችን አስተማሪ በቤታችን ቀጥረው ነው ያስተማሩን፡፡ ከ1ኛ- 8ኛ ክፍል ደግሞ አስፋው ወሰን ት/ቤት ነው የተማርኩት፡፡ ከትምህርት ቤት ጓደኞቼ ጋር በ21 እና በ27 ማህበር አለን፤ ማህበር ሲኖር በየቤታችን አዝማሪ ይቆማል፤ ማስንቆ የሚጫወት፡፡ ወንጂና ናዝሬትም እህቶቼ አሉ፤እዛም እየሄድን እንዝናናለን፡፡ እረ እንደው ተይኝ አልኩሽ —- የተንፈላሰሰ ዘመን ነበር፡፡ በማህበራችሁ ቀን የሚጫወቱት አዝማሪዎቹ የሚታወቁ ነበሩ?
አዎ፡፡ እነ ወረታው፣ ባይረሳው—- እንዴት ቆንጆ ድምፅ አላቸው መሠለሽ፡፡ እነሱ ወደ ቤታችን ሲመጡ ታዲያ ሁሉም ግጥም ሰጪ ነው፤ ሁሉም ተቀባይ ነው፡፡ ቤትም ባይመታም:: ማሲንቆዋቸውን ይዘው ይመጣሉ፤ ጨዋታው ሌላ ነው አልኩሽ፡፡ ደሞዝ እኮ የላቸውም ግን በየወሩ ፅዋ የገባበትን ቤት ስለሚያውቁ ማህበሩ በሚወጣበት ቤት ይመጣሉ፡፡ መጀመሪያ ፀሎት ይደረግና ምሳ ይበላል፣ ከምሳ በኋላ የንስሃ አባቶቻችን ያሳርጋሉ፡፡ ከዛ በኋላ አሸሸ ገዳሜ ነው የእኔ እናት፡፡
ግጥም ከመስጠት ወደ ዘፋኝነት ገባሽ ማለት ነው?
ያን ጊዜ ዘፋኝነትን አልሜው አላውቅም ነበር፡፡ ድምፃዊ ሰይፉ ዮሐንስ የሚባል ወንድም ነበረኝ፡፡ ወላጅ አባታችን ዘፋኝ ሆነ መባልን ሲሰሙ የሞተ ያህል ነው ያለቀሱት:: አለማወቅ እኮ ነው— ማን ያውቀዋል ይሄንን:: አባቴ በጣም አዘኑ…የወንድሜን መታመም ሲሰሙ ግን ድንጋጤአቸው ባሰ፡፡ በጣም በጣም ደግ ልጁ ነበረ፡፡ እርሱም ሞተ፤ አባቴ በጣም ተፀፀቱ — ምን ታደርጊዋለሽ? አለማወቅ ይጎዳል፡፡ ወንድሜ በሞተ በዓመቱ ነው አባታችን የሞቱት፤ በእርሱ ሃዘን (እንባ) ወንድሜ ከሞተ ከአስር ዓመት በኋላ ነው ሙዚቃ የጀመርኩት፡፡
አባቴ ዘፈን አይወዱም ነበር፡፡ ግን በገና ነበራቸው፤ የቅዳም ሱር እለት በገናቸውን አውጥተው ሲደረድሩ ፤የገና ዕለት ጌታን እያመሰገኑ ሲጫወቱ የድምፃቸው ማማር ልዩ ነው —- እናቴም ጥጥ ስትፈትል እያንጎራጎረች ነበር፡፡ ‹‹… ባለድሪ›› የሚለውን ዘፈን ከእርስዋ ነው የወሰድኩት፡፡ ‹‹… ገዳማይ —- ገዳማይ —ገዳማይ›› እያለች ታንጎራጉራለች:: የእናቴን ድምፅ ወንበር ስር ተደብቀን ወይም ግድግዳ ተከልለን ነው የምንሰማት፡፡ እማዬ ድምፅዋ በጣም ነበር የሚያምርው፡፡ አሁን በህይወት የለችም፡፡
እናትሽ የሙዚቃ ስራ ስትጀምሪ በህይወት ነበሩ?
አዎ! ድምፄን የሞረድኩበትን ‹‹አንተ ባለድሪ” የሚል ዘፈን እናቴ ትወደው ነበር፡፡ በአባትዋ ጎንደሬ ስለሆነች ጨዋታው ይስባታል:: የመጀመሪያ የካሴት ስራዬንም እናቴ እንዴት ትወደው ነበር መሰለሽ፡፡
ከዘፈን በፊት ምን ነበር የምትሰሪው?
“ፎር ሽፕ ትራቭል ኤጀንት” የሚባል ድርጅት ውስጥ ትኬት ኤጀንት ሆኜ እሰራ ነበር፡፡ ራስ ሆቴል ዴስክ ነበረችኝ፡፡ እዛ እንግዳ ይመጣል፡፡ እንግዶችን ተቀብሎ
የሚፈልጉትን መረጃ መስጠት፣ መኪና ማከራይት፣ ፎርም ማስሞላት፣ ዲፖዚት መቀበል ነበር ሥራዬ፡፡ ድርጅቱ ከተወሰነ ጊዜ በኋላ ተዘጋ፡፡ በወቅቱ የልጆች እናት፤ የቤተሰብ ሃላፊ ነበርኩ—‹‹ምን ሆኜ ነው የምኖረው..›› ብዬ ሳስብ፣ ጓደኞቼ “እነ በቀለች ክትፎ ከትፈው እየሸጡ ይኖሩ የለ፡፡ ክትፎ ክተፊ›› አሉኝ፡፡
ክትፎ ግን ሞያ ይጠይቃል አይደል–
ሞያ ለእኔ!! እኔ እናትሽ እኮ አንቱ የተባልኩ ባለሞያ ነኝ:: የወላጆቼ ቤት እዚህ ካዛንቺዝ ነበር፡፡ እዛው ጊቢ ውስጥ አንድ ክፍል ተሰጥቶኝ እኖር ነበር፡፡ ክትፎ ቤት ከፈትኩ:: አንድ ቀን ታዲያ ሰዎች ክትፎ ሊበሉ ቀብረር ያለውን ድምፃዊ ከተማ ይፍሩን ይዘውት መጡ፡፡ ያን ቀን አንድ ዕቃ ጠፍቶብኝ ተበሳጭቼ ነበር:: ይሄን ያህል የተበሳጨሽው ምን ቢጠፋብሽ ነው?

አንድ ሙሉ ካርቶን ውስኪ፡፡ አንድ ዘመድ ነበር— አውጥቶ ሽጦብኝ ብስጭት ብዬ ነበር፡፡ አልቅሼ ፊቴን ስጠራርገው የልጅነት መልክ ጥሩ ነው፣ ወለል ‹‹ፏ›› ነው የምለው፡፡ እነ ከተማ ክትፎውን እየበሉ ይጨዋወታሉ:: ከዚያ ከተማ መዝፈን ማንጎራጎር ጀመረ፡፡ እኔም ከጎኑ ቁጭ ብዬ አንጎራጉራለሁ:: ከዛ ከተማ ድንገት ብድግ ብሎ ‹‹እዚህ ቤት ሁለተኛ ክትፎ እንዳይከተፍ›› አለ፡፡
‹‹ምነው አመምዎት?›› አልኩኝ ያልተስማማቸው፣ አለርጂ የሆነባቸው መስሎኝ፡፡
‹‹ይሄን ቆንጆ ድምፅ ይዘሽ በምን ምክንያት ነው የማትዘፍኝው?›› አሉ፡፡
‹‹ድምፅ አለኝ እንዴ?›› አልኩኝ ለራሴ
‹‹ምንድን ነው የምትጠጭው?›› አሉኝ፡፡
እኔ ግን እንኳን በዛ ጊዜ ዛሬም መጠጥ የሚባል አልቀምስም፡፡
‹‹እረ እኔ ምንም አልፈልግም… አልጠጣም›› አልኳቸው፡፡ ሲያስጨንቁኝ
‹‹ኮካ ይሻለኛል›› አልኩኝ፡፡ ያን ጊዜ ግሩም ነበር ኮካኮላ- –ከኮካኮላው ውስጥ ሳላይ ውስኪ ጨምረውብኝ….እንደ ውሃ ጭልጥ አደረኩት፡፡ ከትንሽ ደቂቃ በኋላ ደስ አለኝ… ‹‹እንዴ ምን ሆኜ ነው ደስ ያለኝ…ምን አገኘሁ›› እያልኩ አስብ ነበር፡፡ ለካ ለብታ ማለት ይሄ ነው፡፡ ከዛ በኋላ ሰንጥቄ ሰንጥቄ ለቀቅኩት ዘፈኑን፡፡
የማንን ዘፈን እንደዘፈንሽ ታስታውሺያለሽ?
ከተማ እኔ ቤት የተጫወተውን ባቲ፣ ትዝታን፣ ተይ ማነሽን ተጫወትኩ — ከአሁን በኋላ ‹‹አምቦ ውሃሽን አቀዝቅዥ፣ ቆንጆ ውስኪ አቅርቢ — እኛ እንግዳ ይዘን እንመጣለን —- አበቃ ክትፎ ቤት›› አሉኝ፡፡ ከዛ ምን አለፋሽ — ከአለም አንደኛ ሆንኩኝ፡፡
በማግስቱ የምሽት ክበብ ተጀመረ?
መጀመሩስ ተጀመረ፡፡ መጥተው “በይ ተጫወቺ” ሲሉኝ ከየት ይምጣ፡፡ ያቺ የለችማ የተለመደችው ብረት ለበስ…. ታዲያ ወሰድ አታደርጊም ነበር—
እኔ ምኑን አውቄው—-በፊትም እኮ ወኔዬን ያመጣው ምን እንደሆነ አላውቅም፡፡ በኋላ እኮ ነው የነገሩኝ፡፡ ግን እየለመድኩ መጣሁ —- ሌላ ሆነ እንግዳው፣ ደንበኞቼ በዙ—የብር አቆጣጠሬን ብታይ አስቅሻለሁ፡፡ እንግዶቼን ሸኝቼ ስጨራርስ—-.ብር እቆጥራለሁ፡፡ ‹‹..አንድ.. ሁለት…ሶስት..አራት.. እባካችሁ ተኙ እናንተ ልጆች— መሸ እኮ– ነገ ትምህርት ቤት ወየውላችሁ..›› ብሩ ከእጄ ይንጠባጠባል፡፡
የሽልማቱ ብር ነው?
ሽልማቱ ተይኝ ይረግፍ ጀመር፡፡ ማን አውቆት ቁጥሩን — -ከትራሴ ስር አድርጌው ነው የማድር — ልጆቼ በጠዋት ሲነሱ —-ገንዘቡን ለቃቅመው እየሳቁ ‹‹..አንቺን ብሎ ቆጣሪ›› ብለው ይሰጡኛል፡፡
መኖሪያሽም የስራ ቦታሽም አንድ ቦታ ነበር ማለት ነው? መጀመርያ አዎ፡፡ በኋላ ግን ሃብት መጣ — ካሳንቺዝ እርሻ ሚኒስቴር አካባቢ ቤት ገዛሁ፡፡ ዛሬ ንብ ባንክ ሆኗል:: ታሪኩ ብዙ ነው ባክሽ…በመሃል ታመምኩ፡፡ ሶስት ወር ሙሉ እጅና እና እግሬ ተይዞ ፓላራይዝድ ሆኜ ተኛሁ:: የቤት ስልክ ጮኸና ጨዋታችንን አቋረጠን፡፡ ከካናዳ ወንድ ልጅዋ ነበር የደወለው) ከዚያልሽ — በጠበሉም በምኑንም ብዬ ተሻለኝ፡፡

በመሃል ስራሽን አቁመሽ ነበር?

አዎ ሙሉውን አቁሜ ቤቱን አከራየሁት፡፡ መጨረሻ ላይ ያከራየኋት ሴት እገዛዋለሁ ብላ ስሙን አዛውሬላት ነበረ– -በቼክ አንድ ነጥብ አምስት ሚሊዮን ብር ሰጥታኝ ነበር— ከዚያ እዛ ዱባይ የሚባል አገር ተነስታ ሄደች፡፡ ቤቱ በሃራጅ ተሸጠና ለእኔ ስድስት መቶ ሺ ብር ተሰጠኝ፡፡ ከባንክ በቀኝ እናበግራእጄሶስትመቶሺ፣ሶስትመቶሺብርይዤ ስወጣ በጣም ከበደኝ:: ‹‹ፈጣሪዬ በአቅሜ ነው የሰጠኸኝ.. ያንን አንድ ሚሊዮን አምስት መቶ ሺ ብር..አግኝቼ ቢሆን እንዴት ነበር የምይዘው..ተመስገን ጌታዬ ይሄንኑ በረከቱን ረድዔቱን ስጠው›› ብዬ— (በድጋሚ የቤት ስልክ ጮኸ:: አሁንም ከካናዳ ሌላኛዋ ልጅዋ ደወሎ፤ ሰላምታ ሰጥታ ቆይቶ እንዲደውል ነግራው ዘጋች)

የካሳንቺሱ ስራ ቆመ ማለት ነው —

አንድ ዓመት ይህል ቁጪ አልኩኝ ያለ ስራ፡፡ ከዛም ለምንድን ነው ቁጪ የምትይው ብሎ ቁምላቸው የሚባል የፋሲካ ባለቤት ተቆጣኝ፡፡ ከዛ ኦርጋኔንና የራሴን ባንድ ይዤ እዚያ ሄድኩኝ፡፡ አብረውኝ የሚጫወቱትን ሳክሲፎኒስትና ኦርጋኒስት ይዤ ማለት ነው፡፡ ‹‹ራሄል እዚህ ገብታለች›› ሲባል…ተይኝ አልኩሽ — ሰው እንደጉድ ይጎርፍ ጀመር፡፡

ደንበኞችሽ ታዋቂ ሰዎች፣ ባለሥልጣናትና ባለሃብት— ነበሩ ይባላል፡፡ እንደውም አንዴ ፕሬዚዳንት ግርማ ወልደ ጊዮርጊስን ቃለ መጠይቅ ስናደርግላቸው—.የአንቺን የምሽት ክበብ በጣም ይወዱት እንደነበር ነግረውናል — እጣ ክፍሌም እንደዛ ነገር ነው፡፡ የአዲስ አበባ መሳፍንት መኳንት፣ የራስና የደጃዝማች ልጆች፣ ማን ይቀራል…እገሌ ከእገሌ አልልሽም፡፡ የጨዋ ልጆች ይመጡ ነበር፡፡ ስርዓት ለሌለው እንኳን ስርዓት አስተምሬ ነው የምለከው፡፡ በጃንሆይም ጊዜ ከቤተመንግስት ሰዎች ጋር ነበር ቅርበቴ፡፡ በቃ ይወዱኛል፡፡ ዘፋኝ ሳልሆንም እኮ ነው፡፡

እንዴት ወደ ቤተመንግስት ለመቅረብ ቻልሽ?

ያኔ ቤተመንግስት ቱሪስቶች ሲመጡ አጉራሽ ይፈለግ ነበር:: ቤተ-መንግስት ሄደን እንጀራ እናጎርሳለን፡፡ የቤተመንግስት እንጀራ እንደዚህ ሶፍት ነጭ ነበረ(በእጅዋ የያዘችውን ሶፍት እያሳየችኝ) ፈረንጆቹ ናፕኪን እየመሰላቸው እንጀራውን እንደ ሶፍት ይጠቀሙበታል፡፡ ቤተመንግስት ውስጥ በጣም ስለተቸገሩ— እስኪ ቆነጃጅትን ፈልጉ ተባለ፡፡ አንድ እኔን በጣም የሚያውቅ ሰው ነበረ…ነፍሱን ይማርና ኮማንደር እስክንድር ‹‹ዋይን ገርል ራሄልን ጥሩ›› አለ፡፡
ዋይን ገርል ነበርሽ እንዴ?
አዎ፡፡ ዋይን ስፔሻሊስት ነኝ፡፡
እንዴት— የት ተማርሽው?
ታሪኬ ብዙ ነው አላልኩሽም፡፡
እስቲ አውጊኛ —-
ዛሬ እንግዲህ አብረን ማደራችን ነው፡፡
ግዴለም አጫውቺኝ —-
ስሚ—-.ድሮ ሁለቱን ልጆቼን እንደወለድኩ ባሌን ፈታሁ ከዛ ‹‹ራስ ሆቴል ኮርስ መውሰድ አለብኝ›› ብዬ አሰብኩና ለሶስት ወር ያህል የገበታ ዝግጅት (tabel set up) የእንግዳ መስተንግዶ አሰጣጥ (how to serve the guest) ሰለጠንኩ፡፡ እንግሊዝኛውም ሌላ ነው— እንደ አሜሪካን ነው የምናወራው:: የእኛ ትምህርት ቤት እንደአሁኑ ቀላል መስሎሻል—ከሶስተኛ ክፍል በኋላ በእንግሊዝኛ ነው የምታወሪው፡፡ በተለይ በእንግሊዝኛ አስተማሪ በኩል- —እኛ የተማርንበት ዘመን ሌላ ነበር፡፡ በጣም ቆንጆ ትምህርት ቤት ነው የተማርነው ግን አልሰራንበትም፡፡ እኔን ያልሽ እንደሆነ ግን በጣም የገባኝ አራዳ ስለነበርኩ በወቅቱ ሰርቼበታለሁ፡፡ እና የ‹‹ዋይን ገርል›› ኮርስ ስጨርስ ምርጫ ተሰጠኝና ጊዮንን መረጥኩ፡፡ ያኔ የነበሩት ሆቴሎች በጣም ትንሽ ናቸው፡፡ ዋቢ ሸበሌ ገና እየተጠናቀቀ ነበር:: በተረፈ ጊዮን ሆቴልና ኢትዮጵያ ሆቴል ናቸው፡፡ እኔ ጊዮን ሆቴል ገባሁ፡፡

በአስተናጋጅነት ነው?

ስለ በቬሬጅ (መጠጥ) ነበር ያጠናሁት፡፡ ስለ ኮክቴል አሰራር አውቃለሁ — አንድ መጠጥ ከአንድ መጠጥ ጋር ኮክቴል ይደረጋል፡፡ አፕሬቲቩ፣ ዳይጄስቲቩ—-የተለያዩ የዋይን ዓይነቶች አሉ— ሬድ፣ ዋይት፣ ሮዜ፣ ድራይ፣ስዊት፣ ሚዲየም… ከምን ከምን ምግብ ጋር እንደሚወሰዱ አውቃለሁ፡፡ ካስተመሮቹ በጣም ይደነቁ ነበር፡፡ የት ነው የተማርሽው፤ የት አወቅሽው ይሉኛል፡፡

ስንት ዓመት ሰራሽ በዋይን ገርልነት?

አራት ዓመት ከስድስት ወር ነው የሰራሁት፡፡ ስራውን ብወደውም እየሰለቸኝ መጣ፡፡ አንድ ቀን አኩርፌ ተቀምጬ አንድ ደንበኛችን አዩኝ፡፡ የአርጀንቲና አምባሳደር ነበሩ፡፡ ስሚ—-ብዙ ካስተመሮቼ የሚያውቁኝ በጣም ሳቂታ፣ ደስተኛ፣ ተጫዋች መሆኔን ነው፡፡ የሚያኮርፍም ሰው አልወድም፡፡ ኩርፊያም አልወድም፡፡ ስለዚህ ‹‹ምነው ዛሬ አልሳቅሽም?›› አሉኝ፡፡
‹‹ደከመኝ የሌሊት ስራ ደከመኝ›› አልኳቸው፡፡
“So?” አሉኝ፡፡
‹‹በቃ ሰለቸኝ አስጠላኝ…›› መለስኩላቸው
“Why don’t you come to my embassy, I am go- ing to move by next week.” (ለምን ወደ እኔ ኤምባሲ አትመጪም? በሚቀጥለው ሳምንት እገባለሁ)
እሽ ብዬ ሄድኩ፡፡ እቃ ግዢ ክፍል (ፐርቼዘር) አደረጉኝ:: ከዚያ የጣሊያን ክልስ ፀሃፊና አራት ዘበኞች ቀጠርኩለት፡፡ ሁለት የማታ፣ ሁለት የቀን፡፡ የዘበኞች
ዩኒፎርም(የቤተመንግስት ልብስ ሰፊ ነበር) እሱ ጋ ሄጄ አሰፋሁ፣ ባርኔጣቸውን አሰራሁ:: ሁለት ሾፌሮችም ቀጠርኩ፡፡ የኤምባሲ ሾፌሮች የሚለብሱትን አውቃለሁ:: ወጥ ቤትም ቀጠርኩ—የፅዳት ባለሙያ (ሃውስ ኪፐር) እንዲሁም አትክልተኛ ሁሉ ቀጠርኩ፡፡
ሥራ ብቻ ነው ወይስ ሌላም ግንኙነት ነበራችሁ? ኦኦ—ባለትዳር እኮ ነው፡፡ እኔ ስራውን ነው የፈለግሁት፡፡ (የቤቷ ስልክ ለሦስተኛ ጮኸ…)
እንግዲህ ቻይው—- ልጆቼ አሜሪካና ካናዳ ነው ኑሮዋቸው…ልክ ሲነጋ የኔን ድምፅ ሳይሰሙ ቀናቸውን በስመዓብ አይሉም…(ከአሜሪካ ሴት ልጅዋ ነበረች የደወለችው)—ከተወሰነ ጊዜ በኋላ የአምባሳደሩ ሚስት መጣች፡፡ ይሄኔ ችግር ተፈጠረ፡፡
‹‹ምንድን ነች?›› ብላ አፈጠጠች፡፡
‹‹ይሄን ሁሉ የሰራችው እስዋ ናት›› አሏት፡፡
‹‹ሰዎችን ከመቅጠር ጀምሮ..ፈረስ ቤቱን፣ አበባውን … የቤቱን ቀለም..ይሄን ሁሉ የሰራች እስዋ ናት›› በማለት አስረዷት፡፡ በጣም ሃርድ ወርከር ናት…ብላ ብታደንቀኝም ከጥቂት ጊዜ በኋላ አልተመቸኋትም መሰለኝ—ደሞዜም በጣም ብዙ ነበር፡፡

ምን ያህል ይደርሳል?
2ሺ ብር—
ይሄ ሁሉ ከሙዚቃው በፊት ነው አይደል–

ሙዚቃ ባልታሰበበት ጊዜ እኮ ነው የማወራሽ፡፡ እዚህና እዚያ አስረገጥሺኝ እኮ፡፡ እንዳልኩሽ የሰውየው ሚስት አልተመቸኋትም፡፡ ስርዓት አለኝ—ሰው አከብራለሁ— ሰው ስነሥርዓት ከሌለው አልወድም—ወዲያውኑ ነው የማስወግደው:: ሁለተኛ ማየት አልፈልግም፡፡ እናም‹‹.. በቃ ወደ ውጪ መሄዴ ነው ….›› ብዬ ስነግረው አምባሳደሩ በጣም ደነገጠ፣ ተጨነቀ፡፡ እኔ ግን ትዕግስቴና ፍላጎቴ ተዘግቶ ስለነበር ትቼው ወጣሁ፡፡
ይሄን ሁሉ ያስታወሰን እኮ ለአጉራሽነት ወደቤተመንግስት መግባትሽ ነው—-.የአጉራሽነቱስ ጉዳይ
— አጉራሽነትማ—-ጃንሆይ ጥሩ ጥሩ ልጆችን አምጡ ብለው አዘዙ:: ‹‹እንደውም ጊዮን ሆቴል ሁለት ዌይትረስ አሉ አምጡዋቸው›› ተባለ፡፡ ቤተመንግስት ገብተን ፈረንጆችን እናጎርስ ጀመር፡፡ ፈረንጆቹ..
“Oh my God. What is this? Is this napkin or what?…’” እያሉ ይወናበዱ ነበር፡፡ ስናጎርሳቸው ደስ እንዲላቸው ብለን ፊታቸው እጃችንን እንታጠብ ነበር—-ከዛ ስናጎርሳቸው ተደስተው ሊሞቱ፡፡

ቆንጆ ነሽ—-አድናቆት ምናምንስ አልነበረም?

“you have a beautiful smile, you Ethiopians are beautiful” ይላሉ (ውብ ፈገግታ አለሽ–እናንተ ኢትዮጵያውያን ውብ ናችሁ) —-ምን ልበልሽ— አድናቆት በአድናቆት ነው—-ልዕልቶቹም ያዩናል፡፡ የሆነ ዝግጅት ሲኖር በመካከላቸው ካናፒ እናዞራለን፡፡ ‹‹እንዴት ቆንጆ ናት›› ይሉኝ ነበር፡፡ የአልጋ ወራሽ ሚስት በጣም ያደንቁኝ ነበር፡፡ ልዕልት ተናኘ ወርቅ ነፍሳቸውን ይማረው፡፡ …አረ ተይኝ—አድናቆታቸው ራሱ ገንዘብ ነው፡፡ አክብሮታቸው…ሰላምታቸው…አመለካከታቸው.. ነገረ ስራቸው ሌላ ነበር፡፡

በነገስታቱ ተሸልመሽ ታውቂያለሽ?

እጅግ በጣም ብዙ ሽልማት እንጂ…የአንገት ወርቅ፣ የእጅ ወርቅ አምባር፣እንዲሁም ሰንጋ መግዣ ተብሎ 500 ብር ተሰጥቶኛል:: .የእኔ ልጅ—- ባሳለፍኩት ዕድሜ ቁጭ ማለትን አልወድም፣ የሰው እጅ መጠበቅን አልወድም፣ ስራ መስራት ያስደስተኛል፣ መጫወት መደሰት ቁምነገር መስራት—እጅግ ሰው እወዳለሁ.. ስራ አልንቅም፡፡ የሚገባኝን ነገር አውቃለሁ፡፡ የሰው ነገር አልነካም፡፡ ለዚህም ነው ያልነካሁት የስራ ዓይነት የለም የምልሽ—-.ቆይ ልቁጠርልሽ አርጀንቲና ኤምባሲ፣ ታንዛኒያ ኤምባሲ፣ ፊሊፕስ… ሾው ሩም ውስጥ ሁሉ እሰራ ነበር፡፡ የዋቢሸበሌ ፐርሶኔል አንዴ መብራት ሊገዙ መጥተው ‹‹ምን ልትሰሪ ያለ ፊልድሽ መጣሽ?›› ብለው ዋቢሸበሌ
ወሰዱኝ..እዚያ ስሰራ ደግሞ የሂልተን ሆቴል ..“ፉድና ቤቨሬጅ ማኔጀር” መጡ፣ የውጪ ዜጋ ዋናው የሂልተንን ሃላፊ ጭምር ይዘው፡፡

‹‹ምንድን ነው የምትበሉት?›› አልኳቸው፡፡

‹‹አዘናል›› አሉ፡፡ ያዘዙትን ጠየቅሁ – ስጋ፣ ዶሮ፣ አሳ ነበር ያዘዙት፡፡ ሁለት ዓይነት ወይን ማዘዝ አለባቸው፡፡ አንድ ቀይ ዋይን፣ አንድ ነጭ ዋይን አልኩኝ፡፡ አለበለዚያ ሁለቱንም የሚያባላ ሮዜ ዋይን..አልኩና ሄጄ ጠየቅኋቸው፡፡

‹‹ምንድን ነው የምትጠጡት? ምን ዓይነት ዋይን ላምጣላችሁ?›› አልኳቸው፡፡

‹‹የምንበላውን ካወቅሽ አንቺ ጠቁሚን ምን ይሻለናል?›› አሉኝ፡፡ ሞያዊ ትንታኔ ሰጠኋቸው፡፡ በጣም ተገረሙ፡፡ ኢትዮጵያ ውስጥ እንደዚህ ዓይነት ባለሞያ አለ ብለው ተደንቀዋል፡፡ ከመሄዳቸው በፊት ‹‹ፈቃድሽ ከሆነ..ሰኞ ጠዋት ሂልተን ሆቴል እንድትመጪ›› አሉኝ፡፡

‹‹የት ነው ሂልተን ሆቴል?›› ብዬ ጠየኳቸው፡፡
‹‹እዚህ እዚህ ቦታ….›› ብለው ነገሩኝ፡፡
‹‹እኔ የሆቴል ስራ ሰልችቶኛል..ሆቴል እንዳይሆን ስላቸው..›› ‹‹ኖኖ እንደዚህ አይባልም..ስራ እንደዚህ አይባልም እንድትመጪ..›› አሉኝ፡፡
ሂልተን ሆቴል ሄድኩኝ—“.አይዞሽ ሲደክምሽ ማረፊያ ክፍል እንሰጥሻለን” አሉኝ፡፡ “መቼሽ ቲፑ ሌላ ነው—-በጣም ቆንጆ ቦታ ነው፡፡ የተወሰነ ቦታ ነው የምትሰሪው” ብለው አግባቡኝ፡፡ አሒአ(አዲስ አበባ ሂልተን ሆቴል) የሚል እንዴት ያለ የሚያምር የአበሻ ቀሚስ ተሰራልኝ መሰለሽ —ላይት ብራውን እንደ ጎልዲሽ ዓይነት — አቤት መልክ—አቤት ቁመና…፡፡
ሂልተንስ ስንት ዓመት ሰራሽ?
ከአራት ዓመት በላይ ሰርቻለሁ፡፡

በዘፈኖችሽ ላይ ንጉሶችን ማነሳሳት ትወጂያለሽ —.የጣይቱ ጠጅ ነው…የምኒልክ እልፍኝ– ትያለሽ?
እኔ የሰርቶ አደር ልጅ ነኝ፡፡ ግን እነዚህ አብሬያቸው ያሳለፍኳቸው እንግዶች..ክብር ያላቸው፤ ለሰው ልጅ ጥሩ የሚመኙ፤ ደጎች ናቸው፡፡ እግዚአብሄር ደግሞ የሰውን ልጅ ሲፈጥረው አንድ ነገር ይሰጠዋል…ሁሉን በፕሮግራም ነው የሚፈጥረው፡፡ እግዚአብሄር እኮ እኔን አድሎን ነው እንጂ—እኔ ማን ነኝ I am no body af- ter all. ከማንም አልበልጥም:: ሰው ስለምወድና ስለማከብር… አባቴ ሰርቶ አደርም ቢሆን አስተዳደጋችን እንዴት ሸጋ ነበር — ልጆቼንም በዛ መንገድ ነው ያሰደግኋቸው፡፡

ውጪ አገር ስራዎችሽን አቅርበሽ ታውቂያለሽ?

በፍጹም፡፡ አንድ ጊዜ ብቻ አምባሰል የሚባል ሙዚቃ ቤት ዋሺንግተን ናይት ክለብ ነበረው፡፡ ለስድስት ወር ለመስራት ተስማምቼ ሄጄ —.ለአራት ወር ያህል ከሰራሁ በኋላ ኢትዮጵያኖች እርስ በእርስ ሊጋደሉ ሲሆን ስራውን ትቼ ወደ አገሬ መጣሁ፡፡ ብዙም እንደዚህ ዓይነት ቦታ አይመቸኝም—

የትዳርሽ ጉዳይስ—

ልጆቼን ብቻዬን ነው ያሳደግሁት.— ጠንካራ እናት ነኝ፡፡ .ባሎች ትንሽ አስቸጋሪዎች ነበሩ፡፡ ምን ይጎለኛል—ልጆቼን ለማሳደግ ብዬ ልውሰድም ቢሉ እሽ አልልም—.ይሄው ልጆቼን አሳደግሁኝ ዳርኩኝ–እግዚአብሄር ይመስገን፡፡

የዘመኑን ዘፈኖች ትሰሚያለሽ? እንዴት ነው ዘፈን ድሮ ቀረ ትያለሽ ወይስ —-

ድምፁ የወጣው አሁን ይመስለኛል፡፡ ወጣቶቹ ቆንጆ ቆንጆ ድምጽ አላቸው፡፡ ሲዲውን ስሰማው ጥሩ ነው፡፡ ብዙ ጊዜ የምሰማው ወይ ስለ ሃገር፣ ስለ አንድ ታሪክ፣ ወይም ስለኢትዮጵያ ሊሆን ይችላል፡፡ ኢትዮጵያ ታሪክዋ ሰፊ ነው፡፡ አንዳንዱን እያነሱ አንስቶ መስራቱ ጥሩ ነው፡፡ የፍቅር ነገር መቼም እንዳለ ነው አያረጅም፡፡ ፍቅር ትልቅ ነገር ነው፡፡ ሁልጊዜ ግን ስለ ፍቅረኛ፣ ስለ ባል፣ ስለ ሚስት— ተጣላኝ ታረቀኝ አባረርከኝ…መለስከኝ… እንደዚህ ዓይነት በጣም ሲበዛ ጥሩ አይደለም፡፡ አንችዬ አርጅቼ ይሆን እንዴ? ግን አይደለም…ድሮም ይሄው ነው ስሜቴ…ሁሉም ይቅር እያልኩ አይደለም፡፡ በየመሃሉ ቁምነገር ቢገባበት ማለቴ ነው፡፡ እንጂ ድምፅማ የመጣው አሁን ነው፡፡
በድሮና በአሁን ዘፈኖች መካከል ያለው ልዩነት ምንድን ነው ትያለሽ?

ምርጫቸውና የደረሱበት ቴክኖሎጂ ነው፡፡ በአብዛኛው የፈረንጅ መዚቃ፤ የፈረንጅ ሲኒማ፤ የፈረንጅ ዘፋኞች የሚሆኑትን ነው የሚሆኑት፡፡ ከአሁኑ ዘፋኞች ቴዲ አፍሮን —- ጎንደር ብዙ የተጫወቱ ልጆች አሉ –ማዲንጎ እስከ ወንድሙ…ግሩም ናቸው:: ማዲንጎን ያየሽ እንደሆን የበላይን ታሪክ አስቀምጦታል— በደንብ — ታምር ነው መቼም፡፡ እኔማ ያሳዝነኛል ያንን ሲጫወት:: እነዚህ ቁም ነገር ያላቸው ነገሮች ናቸው፡፡ የኢትዮጵያ ባህል እኮ ተወርቶም አያልቅ፡፡ መጸሐፍም አይችለው፡፡ አስተማሪዎች ያስፈልጋሉ፡፡ እኛ እኮ ድሮ ትምህርት ቤት አሁን ማን ያስተምራል….እዚህም አገር አማርኛ እንደ ሁለተኛ ቋንቋ እየታየ ነው፡፡ እኛ ድሮ በትምህርት ቤት ውስጥ ባንዲራ አውርደን ክፍል እንደገባን ፀሎት እናደርጋለን፤ ከፀሎት በኋላ የሚገባው አስተማሪያችን የግብረገብ ነው፡፡ ከዛ በኋላ ነው ትምህርቱ የሚቀጥለው፡፡
ኢትዮጵያ ከአለም አንደኛ ናት ብል—-.አላፍርም፡፡ስለ ሃገሬ ተናግሬም አልጨርሰው፤አቅሜም አይችለው፡፡ አገራችን፣ ህዝባችን፣ አለባበሳችን፣ ምግባችን፣ አየሩ…በክረምቱ ሰዓት ክረምቱ የታወቀ ነው፤ በበጋው ሰዓት በጋው የታወቀ ነው፣ በበልግ ሰዓት በልጉ የታወቀ ነው፤ አለቀ፡፡ አየራችን ደግሞ ልዩ ነው፡፡ የምታኮራ አገር የሚያኮራ ህዝብ ነው ያለን..ይሄ ራሱ ቢዘፈንለት አይበቃም፡፡

ስንት ካሴት በነጠላ እና በጋራ ሰራሽ..

ወደ 12 ካሴቶችን ሰርቻለሁ፡፡ “ምኒልክ” የሚለው ዘፈኔ ዜማውን የሰራሁት እኔ ነኝ፡፡ የሁሉም ካሴቶቼ ግጥም ድርሰት የይልማ ገብረ አብ ናቸው፡፡
የድምፅሽን ለዛ ስለሚያውቀው በይልማ መርጦ የሚሰጥሽ
አዋ፡፡ ይልማ በአንድ ወቅት አንድ ስራ ገጥሞት አንድ ካሴቴ ላይ ብቻ ሶስት ዘፈኖች የሌላ ሰው ነበሩ፡፡ ከይልማ ጋር ስንሰራ ግጥሞችን መክረንባቸውና ተነጋግረን ነው – ይሄ ይውጣ ይሄ ይግባ ብለን፡፡ አንድ ጊዜ ምን ሆነ…‹‹በደሳሳ ጎጆ ቁጭ ብዬ ብቻዬን ሳለቅስ..›› ምናምን የሚል ግጥም ..መጣልኝ…እኔ እንደዚህ አይነት ነገር …ምንድን ነው በፍፁም አልዘፍንም አልኳቸው፡፡ ችግርም የለብኝ..ይቅርታ አድርጉልኝ የእኔ ስሜት ለእንደዚህ ዓይነት ነገር አይሰራም አልኳቸው፡፡ በጣም ሳቁ..ጭንቅ አልወድም ሌግዠሪ ነገር ነው የምወደው…ዝም ያለ ቆፍጠን ያለ…ለሰውም ቀለል ሲል.. ነው፡፡ የእኔን ለቅሶና ሃዘን ህዝብን ስማልኝ ማለት ምንድን ነው:: የሆነ ድባብ እኮ ይፈጥራል፡፡ ይቅርታ እንግዲህ እኔ እንደዚህ አይነት ታይፕ የለኝም፡፡ ከተሸመ አሰግድ፤ ጋሽ ባህሩ፣ ጋሽ ይርጋ፣ ከተማ መኮንን፣ ዳምጠው…ኡፍ ለዛ አላቸው እኮ፡፡ my God!! የማይሰለቹ እኮ ናቸው፡፡ ስሚ የዛን ዘመን ዘፋኞች..እነ ወረታው… የወረታው ድምፅ እኮ..ራሱ ጊታር ነው፤ ራሱ ሳክስፎን ነው፤ራሱ ቤዝ ጊታር ነው፤ በጣም ጎልደን ድምፅ እኮ ነው ያለው:: ከብዙዎች ጋር ሰርቻለሁ፡፡ ልረሳ ነው እንዴ..እረ አንቺ ልጅ ይሄ ነገር ያሰጋል- — እርጅና መጣ መሰለኝ
ዕድሜሽ ግን ስንት ሆነ?
63 ዓመቴን ባለፈው የፋሲካ ዕለት አከበርኩ.—.ገና ልጅ እኮ ነኝ፡፡ መልካም ልደት፣ ረጅም ዕድሜ ተመኝተንልሻል፡፡ በሶስት መንግስታት ውስጥ በአርቲስትነት ትታወሻለሽ–
የደርግ ጊዜን ሳልነግርሽ፡፡ በምሽት ክበቤ ውስጥ ..እረ ገዳዬ፣ እንደው ዘራፌዋ፣ እንደ ኮሜዲ አድርጌ የምጫወተው ስራ ነበረኝ:: እረ ገዳዬ የሚለውን በእንግሊዝኛ እለው ነበር—

እስኪ አሁን በይልኝ–
Oh killer oh killer
The useless goat give birth to nine
She is died and her children
I love the killer I love the killer
As well as the shooter
When I feel tired I rest under the umberella of ጀግናዬ hair. ብታይ ሰው ይሄን እንደ ኮሜዲ ነው የሚሰማው—-. ትርጓሜው ደግሞ ትክክል ነው፡፡
እረ ገዳዬ አረ ገዳዬ
የማትረባ ፍየል ዘጠኝ ትወልዳለች
ልጆችዋም ያልቃሉ እስዋም ትሞታለች፡፡
ስሚ እኔ ጀግና እወዳለሁ፡፡ ዘፋኝ ባልሆን ወታደር ነበር የምሆነው፡፡ በጣም በጣም ነው ወታደር መሆን.. ለመዝመት አስበሽ አታውቂም ታዲያ–
አይ ልጄቼን ከወለድኩ በኋላ ..ሃላፊነቱም አለ..፡፡
የአሁኑ አልበምሽ..ከስንት ጊዜ በኋላ ወጣ?
ከ7 ዓመት በኋላ…ሰርቼው ቁጭ አድርጌው ነበር…ኮፒ ራይቱም አስጨናቂ ስለነበረ..ሰርቼ ቁጭ አደረኩት:: የምገዛ ሲጠፋ:: አቶ ቁምላቸው ገብረስላሴ የፋሲካ ባለቤት/ የሚሞ ባለቤት…የተፈጠረውን አጫወትኩት፡፡ ከፈቃደ ዋሬ የአምባሰል ሙዚቃ ቤት ባለቤት ጋር እንደ ወንድም ነው የሚተያዩት፡፡ ተነጋገሩና ይሄው ባለፈው ለሰው አፍ አበቁልኝ፡፡
ምን ያህል ገቢ አገኘሽበት ?
እሱን ተይው
ከአሁን በኋላስ ምን ታስቢያለሽ?
አገሬ ላይ ቁጪ ብዬ እግዚአብሄርን ማመስገን ነው… የምስጋና መዝሙር ነው ሃሳቤ፡፡ ደስተኛ ነኝ…እንምታይው ሁሉ ሙሉ ነው..ተመስገን ለእግዚአብሄር ምን ይሳነዋል፡፡ አይንሽን አሞሽ ነበር?
አዎ… ሼክ ሙሃመድ አሊ አሙዲ ናቸው ያሳከሙኝ… የምዘፍነው:: የኢትዮጵያን ህዝብ በሙሉ እወዳቸዋለሁ::
(አዲስ አድማስ ጋዜጣ በ2013 ዓ.ም. ከአርቲስቷ ጋር ያደረገው ቃለ ምልልስ)

The post ድምጻዊት ራሔል ዮሐንስ appeared first on Zehabesha Amharic.

አንድ በ20ዎቹ የእድሜ ክልል የሚገኝ ወጣት አሰቃቂ በሆነ ሁኔታ በዝዋይ እስር ቤት ውስጥ ተገደለ

0
0

Zehabesha News
ኢሳት ዜና :- በአዲስ አበባ 22 እየተባለ በሚጠራው አካባቢ የሚኖረው የ25 ዓመቱ ሲሳይ ተሾመ በቅጽል ስሙ ገብሬ ያለፉትን 8 ዓመታት በቃሊቲና በዝዋይ እስር ቤቶች እየተመላለሰ አሳልፏል።
በተለይ ወደ ዝዋይ እስር ቤት ከተላለፈ በሁዋላ ፣ ሃጎስ የተባለው የእስር ቤቱ ሃላፊ ” አንተ የነፍጠኛ ልጅ እንበቀለሃለን፣ በእኔ እጅ ነው የምትሞተው” እያሉ ይደበድቡትና ይዝቱበት ነበር። ባለፈው ቅዳሜ እናቱ ሊጠይቁት ሲሄዱ፣ ታሞ ሚኒሊክ መወሰዱን ይነግሩዋቸዋል። ወደ ሚኒሊክ ሲሄዱ፣ በአንድ አምቡላንስ ውስጥ ጎንና ጎኑ በኤሌክትሪክ ተጠብሶ፣ ኩላሊቱ አካባቢ ተረጋግጦና በልዞ፣ አናቱ አካባቢ ያረፈበት ድብደባ ፊቱን ለማየት በማይቻል ሁኔታ በደም እንዲሸፈን
አድርጎታል።
የደረሰበትን ጉዳት ለመግለጽ ይዘገንናል የሚሉት ቤተሰቦቹ፣ ፖሊሶች አንዴ ታሟል፣ ሌላ ጊዜ ጉዳዩ በአቃቢህግ ተይዟል በማለት ለመደናገር እየሞከሩ ነው። የ22 አካባቢ ወጣቶች የሟቹ ቲሸርት ያለበትን ፎቶ እያሳተሙ ነው። ፖሊሶችና ደህንነቶች በድንካኑ አካባቢ እየተዘዋወሩ በመቆጣጠር ላይ ናቸው። የሟች የቤተሰብ አባላት የኢትዮጵያ ህዝብ ይፍረደን እያሉ ነው ።

The post አንድ በ20ዎቹ የእድሜ ክልል የሚገኝ ወጣት አሰቃቂ በሆነ ሁኔታ በዝዋይ እስር ቤት ውስጥ ተገደለ appeared first on Zehabesha Amharic.

Health: ግራ የተጋባ የፍቅር ግንኙነት ውስጥ ነኝ፤ እንደምታፈቅረኝ እንዴት እርግጠኛ መሆን እንደምችል ጠቁሙኝና ልወስን!

0
0

አንድ ለ3 ዓመት አብራኝ ለዘለቀች ፍቅረኛ አለችኝ፡፡ ይህቺ ልጅ አፈር ስላት ውሃ ውሃ ስላት ደግሞ አፈር እየሆነች መከራዬን አበላችኝ፡፡ እወድሃለሁ ትላለች፣ ከጥቂት ቀናት በኋላ ደግሞ በስልኬ እንዳትደውል ትላለች፡፡ እሺ ብዬ ዝም ስል ቤቴ ድረስ መጥታ ‹‹አንተ ጨካኝ በእኔ አስችሎህ እኔኮ ያላንተ አይሆንልኝም›› ትላለች፡፡ የመለየት ሐሳብ ሳነሳ ከእኔ ተለይታ መኖር እንደማትችል፣ ከተለየኋት ሥራዋን ጥላ ከሀገር እንደምትጠፋ ትናገራለች፡፡ አብሮ ስለመኖር ሐሳብ ሳቀርብ ‹‹ዕድሜ ልኬን ከአንተ ጋር ስጨቃጨቅ ልኖር…›› እስከማለት ደርሳ ታውቃለች፡፡ የእኔ ፍቅር ደግሞ ከዕለት ዕለት እየጨመረ መጣ፡፡ ሳትደውል ወይም ሳትመጣ ከቀረች ጭንቁን ስለማልችለው፣ በምትሰራበት የቤተሰቧ ሱቅ ዞር ዞር ብዬ ደህንነቷን አረጋግጣለሁ፡፡ እንዲያው አንዳንዴ መስተፋቅር ምናምን የሚሉትን አድርጋብኝ ይሆን እያልኩ አስባለሁ፡፡ ጓደኞቻችን እንኳ ሁኔታችንን አውቀው ‹‹ዛሬ ሰላማዊ ነው››፣ ‹‹ዛሬ የጦር ውሎ ነው›› ምናምን የሚሉት ፈሊጥ አላቸው፡፡ አንዳንዴ ድህነቴን ጠልታ ይሆን ብዬ አስብና በዚህ 3 ዓመት እንኳ ያመጣሁትን ለውጥ አይታ በቅርቡ ትልቅ ደረጃ እንደምደርስ ታስባለች ብዬ ራሴን አፅናናለሁ፡፡ የእኛ ነገር በአጠቃላይ ግራ ያጋባኛል፡፡ እኔ የምላችሁ ይህቺ ልጅ ታፈቅረኛለች ብዬ እርግጠኛ ለመሆን ወይም አታፈቅረኝም ብዬ ራሴን ለመለያየት ምን አድርግ ትሉኛላችሁ? ውሳኔ ሰጥቼ መንገዴን ማስተካከል የሚያስችል ምላሽ ስጡኝ እባካች፡፡
ቲ ነኝ

LOve and Re
ጠያቂያችን ቲ ለሰላምታህ አፀፋዊ ምላሻችንን እየሰጠን በቀጥታ ወደ ምላሻችን እናምራ፡፡

ከጽሑፍህ መረዳት እንደቻልነው፣ ፍቅረኛህ አንዳንዴ እንደምትወድህ ሌላ ጊዜ ደግሞ እንደማትወድህ ትነግርሃለች፣ ይሄም የእሷን እውነተኛ የፍቅር ስሜት እንዳትረዳ አድርጎሃል፡፡ ስለ እውነተኛ አፍቃሪ መለያ መንገዶች ጥቆማና ማድረግ ስላሉብህ ነገሮች ገለፃ ከማለፋችን በፊት ስለ ፍቅር አንዳንድ ስነ ልቦናዊ ትንተናዎችን እናቀርብልሃለን፡፡
አዕምሮአችን እያንዳንዱን ነገር የሚረዳው በምስሎች ነው፡፡ ለምሳሌ አዕምሮህ ውስጥ አበባን የሚወክል ምስል አለ፡፡ ስለሆነም አበባ ስታይ የተመለከትከው ነገር በአዕምሮህ ካለው ምስል ጋር የሚመሳሰል ሲሆን ያ ነገር አበባ እንደሆነ ትረዳዋለህ፡፡ ይህ የሚሆነው ለቁሳዊ ነገሮች ብቻ ሳይሆን ሐሳቦችም ነው፡፡ አዕምሮአችን እያንዳንዱን ሐሳብ ለመገንዘብ ምስሎችን ይጠቀማል፡፡ ለምሳሌ ሰላም የሚለውን ሐሳብ የምንረዳው ለሐሳብ ባስቀመጠው ምስል መሰረት ነው፡፡ ለዚህም ነው ሰዎች በሐሳብ የማይስማሙት- የአንዱ ሐሳብ አንዱ የሳለበት መንገድና ሌላው የሳለበት መንገድ ስለሚለያይ፡፡ ይህን ጉዳይ ወደ ፍቅር ስናመጣው ደግሞ፣ አዕምሮአችን ፍቅር የሚለውን ሐሳብ የሚረዳው ምስልን በመጠቀም ነው፡፡ በስተመጀመሪያ ፍቅር የሚለው ሐሳብ በሆነ ምስል ይወከላል፡፡ ከቆይታ በኋላ አንዲትን ሴት በተደጋጋሚ ስታያት ወይም መቀራረባችሁ ሲጨምር፣ ፍቅር የሚባለው ሐሳብ በልጅቱ ምስል እየተተካ ይሄዳል፡፡ ያኔ ነው እንግዲህ ፍቅር ያዘን የሚባለው፡፡ ስለፍቅር ባሰብን ቁጥር የልጅቱ ምስል እየመጣ ድቅን ይልብናል፡፡ ስለልጀቱ በተደጋጋሚ ባሰብን ቁጥር፣ አዕምሮአችን ያለውን ፍቅርን የሚወክለው የልጅቱ ምስል እየጎላና እየደመቀ ይመጣል፡፡ የፍቅራችን መጠንምእየጨመረ ይመጣል፡፡ እንደ ምሳሌ ያንተን ብንወስድ፣ በደብዳቤህ እንደነገርከን ከልጅቱ ጋር ሶስት ዓመት ቆይታችኋለ፡፡ ይህ የሚነግረን ደግሞ በአንተ አዕምሮ ውስጥ ፍቅር የሚባለው ሐሳብ በልጅቱ ምስል ተወክሏል ማለት ነው፡፡ እየቆያችሁ ስትመጡና ስለሷ ብዙ ስታስብ ደግሞ ፍቅርህ እየጨመረ ሄዷል፡፡

ይህንን ትንተና ወደ አንተ ሁኔታ ስናወርደው ያንተዋ አፍቃሪ እወድሃለሁ ብላህ ትወደኛለች ብለህ በተረጋጋህበት ሰዓት አልወድህም ትልሃለች፡፡ ይህ ደግሞ ስለ ልጅቱ ብዙ እንድታስብ ያደርግሃል፡፡ ስለልጅቱ በተደጋጋሚ አሰብክ ማለት ደግሞ አዕምሮህ ውስጥ ያለው የልጅቱ ምስል እየጎላና እየደመቀ ይመጣል ማለት ነው፡፡ ይህ በእንዲህ እንዳለ አትወደኝም የሚል ድምዳሜ ልትደርስ ስትል እንደምትወድህ ትነግርሃለች፡፡ ይህ ሁኔታ ደግ አሁንም ስለ ልጅቱ የማሰብ ነገር ተጠናክሮ እንዲቀጥል ያደርገዋል፤ ማሰብህ በተራው አዕምሮህ ውስጥ ያለውን እና ፍቅር የሚወክለውን የልጅቱን ምስል እንዲጎላ ብሎም ፍቅርህ እንዲጨምር ያደርገዋል፡፡ በአጠቃላይም የልጅቱ የዛሬ እወድሃለሁ፣ የነገ አልወድህም፣ የከነገ ወዲያ እንደገና እወድሃለሁ ወዘተ… ተግባር አንተን ስልልጅቱ በብዛትና በተከታታይ እንድታስብ አድርጎሃል፡፡ ይህ ሁኔታ ደግሞ አዕምሮህ ፍቅርን የሚወክልበት ምስል በጣም በማጉላቱ ያንተን ፍቅር በእጅጉ ጨምሮታል፡፡ በዚህም አለ በዚያ፣ ልጅቱ አውቃም ይሁን ሳታውቅ አንተን እንድታፈቅራት የሚያደርጉ ተግባራት ከውናለች፣ አንተም በጣም አፍቅረሃታል እንጂ መስተፋቅር ማድረጓን የሚያሳይ ምንም መረጃም ሆነ ማስረጃ የለም፡፡ በመሰረቱ አብሮ ለመኖርም ሆነ በፈቅር ለመዝለቅ ያንተ ፍቅር ብቻ ሳይሆን የእሷም ፍቅር ያስፈልጋልና ቀጥሎ ደግሞ እርሷ ታፈቅረኛለች ወይ የሚለውን ጥያቄ እንዴት መመለስ እንደምትችል አቅጣጫ ልጠቁምህ፡፡

የስነ ልቦና ባለሙያዎች እንደሚያብራሩት ፍቅር ሶት መዋቅሮች አሉትት፡ አንደኛው ቅርብ ግንኙነት የሚባለው ሲሆን ይህም የመቀራረብ፣ አብሮ የመሆን፣በጋራ ነገራትን የመከወን፣ የመገናኘት፣ የመተያየት እና የመሳሰሉ ፍላጎቶችንና ክንዋኔዎችን የሚያጠቃልል ነው፡፡ ሁለተኛው ደግሞ ጥልቅ ስሜት ሲሆን የመፈላለግ፣ የመሳሳም፣ በተፈቃሪው ሁኔታ የመሳብ፣ የወሲህ እና ወዘተ ስሜቶችን የሚያካትት ነው፡፡ ሶስተኛው መስዋዕትነት ሲሆን አንዱ ለሌላው የማሰብ፣ የመጨነቅ፣ በችግር ጊዜ የመድረስ፣ ከራስ ፍላጎት ይልቅ ለሌላኛው ፍላጎት ቅድሚያ የመስጠት፣ ፍቅርን ዘላቂ ለማድረግ አስፈላጊውን ማድረግ/ ለማድረግ መፈለግ፣ ወዘተ የሚይዝ ነው፡፡

ሙሉ ፈቅር የሚባለው ደግሞ እነዚህን መዋቅሮች የሚያሟላ ሲሆንነው፡፡ ስለሆነም ቲ የምታፈቅራት ልጅ ታፈቅረኛለች ወይ የሚለውን ለመመለስ፤ መከወን ያለብህ ተግባር በልጅቱ ውስጥ እነዚህ ሶስት የፍቅር መዋቅሮች መኖቸውን/መታየታቸውን ማረጋጥ ነው፡፡ አንተ ከእሷ ጋር ለመሆን ጥረት ታደርጋለህ፣ እሷስ አካንተ ጋር ለመሆን የመጣር ሁኔታዋ እንዴት ነው? አንተን የመፈለግና አንተ ጋር የመሆን ስሜቷስ ፍቅረኛህ ስትጠፋብህ ሱቋ ድረስ ትሄዳለህ? እሷስ ስትጠፋባት አንተን ለማግኘት ምን አይነት መስዋዕትነት ትከፍላለች? አንተን ለመደገፍ ምን ያህል ትጥራለች? በችግር ጊዜህ የመድረስ ሁኔታዋና ፍጥነቷ የት ድረስ ነው? እና የመሳሰሉ ጥያቄዎችን ለራስህ በመጠየቅና ተግባራቶቿን በመመዘን ልጅቱ ታፈቅረኛለች አታፈቅረኝም የሚለውን መለየት ትችላለህ፡፡ ነገሩ እንዲህ እደምፅፍልህና እንደምታነበውም ቀላል አይደለም፡፡ ይልቁንም ትልቅ ሥራንና አስተዋይነትን የሚጠይቅ ተግባር ነው፡፡ ጊዜ ወስደህ ቁጭ በልና ሶስቱን መዋቅሮች ወረቀት ላይ ፃፍ፡፡ እያንዳንዱን መዋቅር እንዴት መለካት እንደምትችል በጥልቀት አስብና በመዋቅሩ ስር መለኪያ ጥያቄዎችን ወረቀቱ ላይ አስፍር፡፡ በመቀጠል በአፍ የምትነግርህን ሳይሆን ተግባራቷን አጥና፡፡ ከጥናትህ በመነሳት በእያንዳንዱ መዋቅር ስር ያለፈችባቸው ላይ / ምልክት፣ ያላለፈችበት ላይ የX ምልክት አስቀምጥ፡፡ ምሳሌ ሰጥቼ ላስረዳህ፡፡ የፍቅረኛህን የመስዋዕት መዋቅር ለመመዘን ‹‹በችግሬ የመድረስ ሁኔታዋ እንዴት ነው?›› የሚል ጥያቄ አዘጋጅ፡፡ ይህንን ጥያቄ ለመመለስ ስልክ ደውልና አሞኝ ቤቴ ተኝቻለሁ ብለህ ንገራትና በቀጣይ የምታደርገውን ተግባር ተመልከት፡፡ ወደ ቤትህ መጥታ መንከባከብ፣ ያን ካልቻለች ደግሞ ስልክ እይደወለች ታከምክ? መድሃኒትህን ወሰድክ? ምግብ በላህ? ወዘተ አይነት ክትትል ካደረገች ይህንን ካልቻለች ደግሞ ሰዎችን በመላክ ስላንተ ሁኔታ ክትትል ካደረገች፣ ወዘተ በጥያቄው ትይዩ የ/ ምልክት ታደርጋለህ፡፡ የማታደርግ ከሆነ ደግሞ X ምልክት ታደርጋለህ ወይም ሌላ መመዘኛ (ለምሳሌ ስራህ ላይ ያጋጠመህን ችግር መንገር) በመጠቀም ለጥያቄህ ምላሽ ለማግኘት ትሞክራለህ፡፡ በተመሳሳይም እያንዳንዱን ጥያቄ በዚህ መልኩ ትመስንና በስተመጨረሻ አጠቃላይ ምዘነሃን በማስቀመጥ ትወደኛለች ወይም አትወደኝም ወደሚል ድምዳሜ መድረስ ትችላለህ፡፡

እዚህ ላይ ሁለት ነገሮችን ልጠቁምህ፡፡ አንደኛ ለአዘጋጀኸው ጥያቄ ምላሽ ለማግኘት እሷን አትጠይቅ፡፡ ይልቁንም ከምታወራውና ከምትሰራው የራስህን ፍርድ/ግምት ውሰድ፡፡ ሁለተኛው ነገር የእሷን ሁኔታ ስትገመግም/ስትመዝን ነገራትን ሁሉ ልክ እንዳንተ ካደረገች መመዘኛውን እንዳላለፈች ከመቁጥር ተቆጠብ፡፡ ምክንያቱም የአንተ እና የእሷ ፍቅር አንድ ላይሆን ይችላል፡፡ ወይም እሷ የፍቅር መግለጫ የምትለው ተግባርና አንተ የፍቅር መግለጫ የምትለው ተግባር የተለያየ ሊሆን ይችላልና፡፡ ለምሳሌ አንተ ፍቅረኛህ ስትጠፋብህ ስራ በቦታዋ በመሄድ እሷን ለማየት መስዋዕት ትከፍላለህ፡፡ በተመሳሳይ አንተ ስትጠፋ እሷ ያንተ የሥራ ቦታ ስላልመጣችና ስላላየችህ መስዋዕት ለመክፈል ዝግጁ አይደለችም አትበል፡፡ ይልቁንም መስዋዕት መክፈሏን የሚያሳዩ ሌሎች ተግባራትን ተመልከት፡፡

ውድ ጠያቂያችን ለሰጠኸን ጥያቄ በቂ ምላሽ እንደሰንህ ተስፋ እናደርጋለን፡፡ ነገር ግን አንድ አብይ ነገር እናንሳ፡፡ በፅሑፍህ እንደገለፅከው የልጅቱ ባህሪ ይለዋወጣለ፡፡ በዚህ ሁኔታ ደግሞ አንድን ሁኔታ ለማረጋገጥ ስትሞክር በአንድ ጊዜ ባህሪዋ ብቻ መመዘን ወደተሳሳተ ድምዳሜ ሊወስድህ ይችላል፡፡ ስለሆነም ለአንድ ጥያቄ መልስ ለመስጠት ምዘናህን በሁለትና ከዛ በላይ በሆኑ መለኪያዎች ለካ ባይ ነኝ፡፡ በስተመጨረሻ መልካም የለውጥ እና የፍቅር ጊዜ እየተመኘኹልህ እሰናበትሃለሁ፡፡ ቻው!

The post Health: ግራ የተጋባ የፍቅር ግንኙነት ውስጥ ነኝ፤ እንደምታፈቅረኝ እንዴት እርግጠኛ መሆን እንደምችል ጠቁሙኝና ልወስን! appeared first on Zehabesha Amharic.

Sport: ከማንቸስተር ሲቲ ማን ለቅቆ ማን ይቀጥላል?

0
0

Man. City
በቀጣዩ የውድድር ዘመን ከኤቲሃድ የሚለቅቁት እና ወደ ክለቡ የሚገቡት እነማን ይሆኑ?
ዊሎ ካባሌሮ (ግብ ጠባቂ)
ዕድሜ፡- 33
ፈረመ፡- 2014 (6 ሜ.ፓ)
ተሰልፎ ተጫወተ፡- 2
ከባሌሮን ያስፈረሙት ፔሌግሪኒ ናቸው፡፡ በማላጋ አብሯቸው የሰራው ግብ ጠባቂ የጆ ሃርት ተጠባባቂ እንዲሆን ቡድኑን የተቀላቀለው በቺሊያዊው ይሁንታ ነው፡፡ አርጀንቲናዊው ከጉዳት ርቆ በበርካታ ጨዋታዎች ላይ የመሰለፍ ዕድሉ ውስን ነው፡፡ በመሆኑም የሃርት ተጠባባቂ ለመሆን የሚመጥን ይመስላል፡፡
ብይን፡- ለተጨማሪ የውድድር ዘመን በክለቡ ሊቆይ ይችላል፡፡
ይህን ያውቃሉ፡- ካባሌሮ ተሰልፎ በተጫወተባቸው ሁለት ግጥሚያዎች ላይ (ሰንደርላንድ እና ሃል) በእያንዳንዳቸው ሁለት ጎሎች ተቆጥረውበታል፡፡ እንደዚያም ሆኖ ቡድኑ ሁለቱን ጨዋታዎች አሸንፏል፡፡
ጆ ሃርት (ግብ ጠባቂ)
ዕድሜ፡- 27
ፈረመ፡- 2006 (500 ሺ.ፓ)
ተሰልፎ ተጫወተ፡- 30
ከማንቸስተር ዩናይትድ ጋር በተደረገው ጨዋታ ላይ በምርጥ ብቃቱ ላይ አልነበረም፡፡ ነገር ግን የእንግሊዙ ግብ ጠባቂ ሌሎቹ በዙሪያው ያሉ ተጨዋቾች ተዳክመው በታዩበት ወቅት እንኳን አቋሙን ጠብቆ ዘልቋል፡፡ በመጪው ክረምት ሲቲ ቡድኑን እንደ አዲስ የሚያዋቅር ከሆነ ያለምንም ጥርጥር ሃርት የቡድኑ ዋነኛ አካል ይሆናል፡፡
ብይን፡- በእርግጠኝነት ይቆያል
ይህን ያውቃሉ?:- በዚህ የውድድር ዘመን ሃርት ከየትኛውም የሲቲ ተጨዋች በላይ በፕሪሚየር ሊግ በርካታ ደቂቃዎችን (2700) ተሰልፎ ተጫውቷል፡፡
ጋኤል ክሊቺ
(የመስመር ተከላካይ)
ዕድሜ፡- 29
ፈረመ፡- 2011 (7 ሚ.ፓ)
ተሰልፎ ተጫወተ፡- 23
ጎል፡- 1
በአንድ ወቅት ጥሩ መንፈስ ያለው ጎበዝ ተጨዋች ነበር፡፡ ነገር ግን የብቃቱ ጣሪያ ላይ የነበረበት ጊዜ አልፏል፡፡ በመሆኑም ሲቲ በግራ መስመር ተከላካይ ስፍራ መላ ማፈላለግ ግድ ይለዋል፡፡ አለበለዚያ በቀጣዩ የውድድር ዘመንም ቢሆን ለዋንጫ ተፎካካሪ አይሆንም፡፡
ይህን ያውቃሉ?:- በዚህ የውድድር ዘመን ከ50 በላይ ሸርተቴዎችን ከወረዱ የሲቲ ተጨዋቾች መካከል የእርሱን ያህል ውጤታማ የነበረ የለም፡፡ 81 በመቶ የሚሆኑት ስኬታማ ነበሩ፡፡
Manchester City FC v FC Bayern Muenchen - UEFA Champions League
ማርቲን ዴሚቼሊስ
(የመሀል ተከላካይ)
ዕድሜ፡- 34
ፈረመ፡- 2013 (4.2 ሜ.ፓ)
ተሰልፎ ተጫወተ፡- 25
ጎል፡- 1
ሲቲን የተቀላቀለ ሰሞን ክፉኛ ተተችቷል፡፡ በዚህ የውድድር ዘመን ግን የቡድኑ ምርጥ ተከላካይ እርሱ ነው፡፡ ዕድሜው የገፋውን ቡድን ለማስወገድ ከተንቀሳቀሱ ግን ዕድሜው ደንቃራ ሊሆንበት ይችላል፡፡
ብይን፡- ለሲቲ ጥሩ ግልጋሎት ሰጥቷል፡፡ ለእርሱ የመውጫውን በር ለማሳየት መጣደፍም አያስፈልግም፡፡ ነገር ግን የክለቡ የረዥም ጊዜ እቅድ አካል እደማይሆን እርግጥ ነው፡፡
ይህን ያውቃሉ?:- በ2014/15 ደሚቼሊስ 131 ጊዜ ኳስን ከአደጋ ክልል በማፅዳት ከቡድኑ ጓደኞቹ ሙሉ ቀዳሚ ነው፡፡
አሌክሳንደር ኮላሮቭ
(የመስመር ተከላካይ)
ዕድሜ፡- 29
ፈረመ፡- 2008 (19 ሚ.ፓ)
ተሰልፎ ተጫወተ፡- 15
ጎል፡- 8
በአሁኑ ወቅት ከቡድኑ አሰላልፍ ርቋል፡፡ በየትኛውም የረዥም ጊዜ እቅድ ውስጥ የመካተት ዕድል የለውም፡፡
ብይን፡- ከቡድኑ የመልቀቂያ ትክክለኛ ጊዜው ነው፡፡
ይህን ያውቃሉ?:- ኮላሮቭ በዚህ የውድድር ዘመን እስካን ጎል አላስቆጠረም፡፡ ከሲቲ ጋር ባሳለፋቸው ያለፉት አራት የውድድር ዘመናት በእያንዳንዳቸው ቢያንስ አንድ ጎል አስቆጥሯል፡፡
ቪንስ ኮምፓኒ
(የመሐል ተከላካይ)
ዕድሜ፡- 29
ፈረመ፡- 2008 (6 ሜ.ፓ)
ተሰልፎ ተጫወተ፡- 23
ጎል፡- 0
የክለቡ መሪ እና አምበል ደካማ የውድድር ዘመን እያሳለፈ ይገኛል፡፡ በዋናነት እንደምክንያት የተጠቀሱት ጉዳት እና የአቋም መውረድ ናቸው፡፡ በዚህ ምክንያት ተጋላጭ ያልነበረው የኋላ መስመር ድብደባ ያስተናግድ ጀመር፡፡ ካምፓኒ ያለ ውድድር በሚያሳልፈው ክረምት ይጠቀም ይሆናል፡፡
ምናልባት ዘንድሮ ተቀዛቅዞ የታየው የዓለም ዋንጫ ላይ በመሳተፉ እና ተደራራቢ ጨዋታዎችን በማድረጉ ይሆናል፡፡ ሲቲዎች የተወሰነ እረፍት የቀድሞውን ኃይሉን ይመልስለታል ብለው ተስፋ ያደርጋሉ፡፡
ብይን፡- የልዩ ብቃት እና ሰብዕና ባለቤት የሆነውን ተከላካይ ለማሰናበት ጊዜው አልደረሰም፡፡ በቀጣዩ የውድድር ዘመን በክለቡ ይቆያል፡፡
አሊያኪውም ማንጋላ
(የመሀል ተከላካይ)
ዕድሜ፡- 24
ፈረመ፡- 2014 (32 ሚ.ፓ)
ተሰልፎ ተጫወተ፡- 19
ጎል፡- 0
በ32 ሚሊዮን ፓውንድ ፖርቶን ለቅቆ ሲቲን የተቀላቀለው ተከካላይ የታሰበውን ያህል ውጤታማ አልሆነም፡፡ ተጫዋቹ ለእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የሚመችም አይመስልም፡፡ ዝውውሩ በኤትሃድ ሂቱን በሚመሩ ሰዎች ላይ ጥያቄ የሚያስነሳ ነው፡፡
ብይን፡- ለኃላፊነቱ የሚመጥን አይመስልም፡፡ ጥፋትን መቀነስ ብልህነት ይሆናል፡፡ ነገር ግን ሲቲ ለተጫዋቹ ከከፈለው የዝውውር ገንዘብ ጋር ተቀራራቢ የሆነ መጠን ያለው ሂሳብ ለማቅረብ የሚደፍር ያለ አይመስልም፡፡
ይህን ያውቃሉ?:- ማን ጋላ በዚህ የውድድር ዘመን በራሱ ሜዳ አጋማሽ ካደረጋቸው ፓሶች መካከል 94 በመቶ የተላኩ ነበሩ፡፡ ይህ አሃዝ ከየትኞቹም የሲቲ ተከላካዮ ይበልጣል፡፡
ባካሪ ሳኛ
(የመስመር ተከላካይ)
ዕድሜ፡- 32
ፈረመ፡- 2014 (በነፃ)
ተሰልፎ ተጫወተ፡- 9
ጎል፡- 0
ሳኛ አርሰናልን ለቆ የማንቸስተሩን ሃሳብ ሲቀላቀል የፈረመው የሶስት ዓመት ኮንትራት ነው፡፡ ፔሊግሪኒ በብዙዎቹ ትልልቅ ጨዋታዎች ላይ ተጠቀመውበታል፡፡ ነገር ግን ወጣት አማራጮችን መፈለግ ብልህነት ነው፡፡ በቀጣዩ የውድድር ዘመን የመጀመሪያ ተሰላፊ የመሆን ዕድሉ የጠበበ ነው፡፡
ብይን፡- በጭራሽ የመጪው ጊዜ እቅድ አካል ሊሆን አይችልም፡፡ ነገር ግን ተጠባባቂ ሆኖ ሊቀጥል ይችላል፡፡
ይህን ያውቃሉ?:- ሳኛ በሲቲ ባሳለፈው የመጀመሪያ የውድድር ዘመን በፕሪሚየር ሊግ ላይ የመሰለፍ ዕድል ያገኘው በዘጠኝ ጨዋታዎች ብቻ ነው፡፡ አሸንፎ መውጣት የቻለው ደግሞ በአራቱ ብቻ ነው፡፡
ፓብሎ ዛባሌታ
(የመስመር ተከላካይ)
ዕድሜ፡- 30
ፈረመ፡- 2008 (6.5 ሚ.ፓ)
ተሰልፎ ተጫወተ፡- 23
ጎል፡- 1
በደጋፊዎች እጅግ ከሚደዱት ተጨዋቾች አንዱ የሆነው አርጀንቲናዊ ድንቅ የሚባል የውድድር ዘመን በማሳለፍ ላይ አይገኝም፡፡ ዛባሌታ ከጠንካራ ማንነት የተሰራ በመሆኑ ችግሮቹን ቀርፎ በቀጣዩ የውድድር ዘመን የብቃቱ ጣሪያ ገና እንዳላለቀ ሊያስመሰክር ይችላል፡፡
ብይን፡- እርሱ የሚገኘው ካምፓኒ በሚገኝበት ምድብ ነው፡፡ በሲቲ የውጤታማነት ዘመን የቡድኑ ቁልፍ ተጨዋቾች ከነበሩት አንዱ እርሱ ነው፡፡ በመሆኑም በአንድ የውድድር ዘመን ጥሩ አቋም አላሳየም ብሎ ማሰናበት ችኩልነት ይሆናል፡፡
ይህን ያውቃሉ?:- ከአምስት በላይ ጨዋታዎችን ካደረጉ የሲቲ የሜዳ ላይ ተጨዋቾች መካከል ተቀይሮ ወደ ሜዳ ያልገባም ሆነ ተቀይሮ ያልወጣ ብቸኛ ተጨዋች ቢኖር እርሱ ብቻ ነው፡፡
ፈርናንዲንሆ (አማካይ)
ዕድሜ፡- 29
ፈረመ፡- 2013 (30 ሚ.ፓ)
ተሰልፎ ተጫወተ፡- 27
ጎል፡- 2
ጥበበኛ ተጨዋች አይደለም፡፡ ነገር ግን የሚተማመኑበት አማካይ ነው፡፡ ማንኛውም ቡድን በስኳዱ ሲገናኝ ውጤታማ ላይሆን ይችላል፡፡ ነገር ግን በስኳዱ ውስጥ ቢኖር ጠቃሚ መሆኑ አያጠራጥርም፡፡
ብይን፡- በቀጣዩ የውድድር ዘመንም የቡድኑ አካል መሆን ይችላል፡፡
ይህን ያውቃሉ?:- ፈርናንዲንሆ ለ347 ኳሶች አንድ ለአንድ ተፋልሞ በ173 በበላይነት ወጥቷል፡፡
ፈርናንዶ (አማካይ)
ዕድሜ፡- 27
ፈረመ፡- 2014 (12 ሚ.ፓ)
ተሰልፎ ተጫወተ፡- 21
ጎል፡- 2
ሌላኛው በ12 ሚሊዮን ፓውንድ ለሲቲ የፈረመ ያልተሳካ ዝውውር ነው፡፡ ቀርፋፋ ከመሆኑ በተጨማሪ ኳስን ወደ ፊት ፓስ የማድረግ ጥላቻ ያለበት ይመስላል፡፡ ወደ ሲቲ ምን ይዞ መጣ ወይም ሲቲ ምን ያስገኝልኛል ብሎ አስረመው? መልስ ያልተገኘለት ጥያቄ ይህኛው ነው፡፡
ብይን፡- ገዢ ከተገኘ ይለቀቃል፡፡
ይህን ያውቃሉ?:- ፈርናንዶ 62 በመቶ የማሸነፍ ንፃሬ አለው፡፡ እርሱ ባልተሰለፈበት ጨዋታ ሲቲ የሚያሸንፈው በ43 በመቶ ብቻ ነው፡፡
ጀምስ ሚልነር (አማካይ)
ዕድሜ፡- 29
ፈረመ፡- 2010 (26 ፣.ፓ)
ተሰልፎ ተጫወተ፡- 27
ጎል፡- 3
ከሚገባው በታች ግምት የሚሰጠው ድንቅ ተጨዋች ነው፡፡ ነገር ግን ከማንቸስተር ሲቲ ጋር አዲስ ኮንትራት መፈራረም ባለመቻሉ ክለቡን መልቀቁ አይቀርም፡፡ አሰልጣኙ የሚፈልጉት አይነት ተጨዋች ነው፡፡ የሚለቀቅ ከሆነ በርካታ የሚያስፈርሙት የሚችሉ ክለቦች አሉ፡፡
ብይን፡- በክለቡ መቆየት ነበረበት፡፡ ነገር ግን ያ የሚሆነው አይመስልም፡፡
ይህን ያውቃሉ?:- በዚህ የውድድር ሲቲ ባስቆጠራቸው ዘጠን ጎሎች ላይ ተሳትፎ አድርጓል፡፡ በሲቲ በነበረው ቆይታ ከዚህ ቀደም ይህንን አይነት ስፖርት አስመዝግቦ አያውቅም፡፡
ሳሚር ናስሪ (አማካይ)
ዕድሜ፡- 27
ፈረመ፡- 2011 ()24 ሚ.ፓ
ተሰልፎ ተጫወተ፡- 22
ጎል፡- 2
አልፎ አልፎ ካበረከታቸው ውስጥ አስተዋፅኦዎች በስተቀር ከእንደሱ ያለ በተሰጥኦ የታደለ ተጫዋች ከሚጠበቀው በታች እየሰጠ ያለ አማካይ ነው፡፡ ይህ በራሱ የውድድር ዘመኑን የሲቲ ሁኔታ ያንፀባርቃል፡፡
ብይን፡- በሲቲ አላማውን ከግብ አድርሷል፡፡ ጥሩ ክፍያ ፈፅሞ የሚወስደው ቢገኝ እንደ ትልቅ ኪራ አይቆጠርም፡፡
ይህን ያውቃሉ?:- በዚህ የውድድር ዘመን ሲቲ ናስሪ ከተሰለፈባቸው ጨዋታዎች 59 በመቶ አሸንፏል፡፡ እርሱ በሌለበት ግን የማሸነፍ ንፃሬው 50 በመቶ ብቻ ነው፡፡
ሄሱስ ናቫስ
(የመስመር ተጨዋች)
ዕድሜ፡- 29
ፈረመ፡- 2013 (14.9 ሜ.ፓ)
ተሰልፎ ተጫወተ፡- 30
ጎል፡- 0
ከሲቪያ ሲመጣ ከፍተኛ ግምት ተሰጥቶት የነበረ ቢሆንም ተስፋ የተጣለበትን ያህል መሆን አልቻለም፡፡ በዚህ የውድድር ዘመን 30 ጨዋታዎች ላይ ተሰልፎ አንድም ጎል አለማስቆጠሩ በራሱ የሚነግረን ነገር አለ፡፡
ብይን፡- ትክክለኛ ጥያቄ የሚያቀርብ ወገን ከተገኘ አደጋ ላይ ነው፡፡ 29 ዓመት ስለሞላው ከዚህ የተሻለ አቋም የማሳየት ዕድሉ ጠባብ ነው፡፡
ይህን ያውቃሉ?:- በዚህ የውድድር ዘመን ናቫስ ሰባት ጎል የሆኑ ኳሶችን አመቻችቶ አቀብሏል፡፡
ያያ ቱሬ (አማካይ)
ዕድሜ፡- 31
ፈረመ፡- 2010 (24 ሚ.ፓ)
ተሰልፎ ተጫወተ፡- 24
ጎል፡- 8
ትልቁ እንቆቅልሽሽ፡ ለዓመታት የሲቲ ስኬታማነት የነበረው ተጨዋች በዚህ የውድድር ዘመን የተሰላቸ የደከመ እና ከቡድኑ የተነጠለ መስሏል፡፡ የቀድሞ ማንነቱን ጥላ መስሏል፡፡ ሲቲ የእርሱን ግልጋሎት አጥብቆ በሚፈልግበት ወቅት ኃላፊነቱን መሸከም እየከበደው መጥቷል፡፡ ለሲቲ የፈፀመውን ነገር ክብር ሊነፍግ የሚሞክር የለም፡፡ ነገር ግን የሲቲ እና ቱሬ መለያያ የደረሰ ይመስላል፡፡
ብይን፡- እንደ ኢንተር ሚላን አይነት ቡድን ጥሩ ጥያቄ ካቀረበ እርሱን በሌላ የመተኪያው ትክክለኛ ወቅት ደርሷል፡፡
ይህን ያውቃሉ?:- ቱሬ በዚህ የውድድር ዘመን ከየትኛውም የሲቲ ተጨዋች በላይ ኳስ ነክቷል፡፡
ዴቪድ ሲልቫ (አጥቂ)
ዕድሜ፡- 29
ፈረመ፡- 2010 (26 ሚ.ፓ)
ተሰልፎ ተጫወተ፡- 26
ጎል፡- 11
ምናልባት በዚህ የውድድር ዘመን ከዚህ በፊት ካሳየው ድንቅ ብቃት ጋር የሚስተካከል እንቅስቃሴ አላደረገ ይሆናል፡፡ ነገር ግን በየትኛው ሰዓት ልዩ ነገር መሥራት የሚችል ምትሃተኛ እግርኳስ ተጨዋች ነው፡፡ ፕሪሚየር ሊጉን ማድመቁንም ይቀጥላል፡፡
ብይን፡- ይቆያል፡፡

The post Sport: ከማንቸስተር ሲቲ ማን ለቅቆ ማን ይቀጥላል? appeared first on Zehabesha Amharic.

ካድሬዎች የምርጫ ካርድ ላይ ንብን እየለጠፉ ለመራጩ እያደሉ ነው

0
0


EPRDF
በጋሞጎፋ ዞን ቁጫና ቦርዳ ወረዳዎች የደኢህዴን/ኢህአዴግ ካድሬዎች የህዝቡን ካርድ እየተቀበሉ የምርጫ ካርዱ ላይ የንብን ምልክት በስቴፕለር በማያያዝ ኢህአዴግን እንዲመርጡ እያስገደዱ እንደሚገኙ በጋጎፋ ዞን የሰማያዊ ፓርቲ አስተባባሪ አቶ ወንድሙ መኩሪያ ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡ ካድሬዎቹ ህዝቡን 1ለ5 በማደራጀት የንብ ምልክት የተለጠፈበት ካርድ በማደል ‹‹የምትመርጡት ኢህአዴግን ነው›› እያሉ እያስገደዱ እንደሚገኙ ገልጸዋል፡፡

የዞኑ፣ የወረዳውና የየ ምርጫ ክልሉ ምርጫ አስፈጻሚዎች ካድሬዎቹ የንብ ምክትን የምርጫ ካርዱ ላይ እያያያዙ ኢህአዴግን እንዲመርጡ እያስገደዱ መሆኑን ቢያውቁም ምንም እርምጃ እየወሰዱ አይደለም ብለዋል፡፡

በሌላ በኩል በጋሞጎፋ ዞን ቦረዳ ወረዳ ሰማያዊ ፓርቲ እሁድና ቅዳሜን ‹‹የገበያ ቀን ስለሆነ›› በሚል ቅስቀሳ እንዳያደርግ መከልከሉን አስተባባሪው ገልጸዋል፡፡ ‹‹የምርጫ ህጉ የሚለው ቅስቀሳ መደረግ ያለበት ከገበያ 500 ሜትር ርቆ ነው እንጅ በገበያ ቀን ቅስቀሳ አይደረግም አይልም፡፡ እኛን ግን ገበያ በሌለባቸው ቦታዎች ሁሉ እሁድና ቅዳሜ ቅስቀሳ እንዳናደርግ ከልክለውናል›› ብለዋል፡፡ ሰማያዊ ፓርቲ ቅስቀሳ እንዳያደርግ እየከለከሉ የሚገኙት የቦረዳ ወረዳ የፀጥታ አስተዳደር ኃላፊ አቶ ማርካ ማዶ እና የወረዳው ፖሊስ አዛዥ መቶ አለቃ ታምራት ናቸው ብለዋል፡፡

The post ካድሬዎች የምርጫ ካርድ ላይ ንብን እየለጠፉ ለመራጩ እያደሉ ነው appeared first on Zehabesha Amharic.

ጆሲ ኢንዘሓውስ ሾው ለኢቢኤስ ቴሌቪዥን ማስጠንቀቂያ ጻፈ “ከግንቦት 30 ጀምሮ በእናንተ አስገዳጅነት ፕሮግራማችንን እናቋርጣለን”

0
0

jose in ze house1
ጆሲ እንዘሓውስ ሾው ለኢቢኤስ ቴሌቪዥን በላከው ግልጽ ደብዳቤ በቴሌቪዥን ጣቢያው አስገዳጅነት ፕሮግራሙን ከግንቦት 30 ጀምሮ እንደሚያቋርጥ አስታወቀ:: ሙሉ ደብዳቤውን ያንብቡት::

ጉዳዩ፡ፕሮግራም ስለማቋረጥ

ድርጅታችን ከጣቢያችሁ የአንድ ሰዓት የስርጭት ጊዜ በመውሰድ በ ኢቢኤስ ቴሌቪዥን ላለፉት ሁለት ዓመታት “ጆሲ ኢን ዘ ሃውስ ሾው ” የተሰኘ ፕሮግራም እያቀረበ እንደሚገኝ ይታወቃል፡፡ ፕሮግራሞቻችን ሀገራዊ ፋይዳ ያላቸው፤ ትውልድን የሚያንጹና የሚያስተምሩ በመሆናቸው በአጭር ጊዜ ውስጥ በተመልካች ዘንድ ከፍተኛ ተወዳጅነት ለማግኘት የቻሉ እንደሆነ አያጠራጥርም፡፡ቀደም ባለው ጊዜ በተፈቀደልን የአየር ሰዓት የሠራናቸውን ፕሮግራሞች ለማቅረብ የነበሩት ሁኔታዎች የተመቻቹ ቢሆንም ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ ግን አየር ላይ እንዲውሉ ከላክናቸው ፕሮግራሞች አንዳንዶቹ በተፈቀደልን የአየር ሰዓትና ጊዜ እንዳይተላለፉ ተደርገዋል፡፡

ጆሲ መልቲሚዲያ የሚያዘጋጃቸው ፕሮግራሞች የአየር ሰዓት ለመሸፈን ብቻ ተብለው የሚዘጋጁ ሳይሆን እያዝናኑ የሚያስተምሩ ኢትዮጽያዊ አንድነትን የሚያጠነክሩ ፤የትላንትን ታሪክ የሚያውሱና ትውልድ የሚቀርጹ፤ መረዳዳትንና መተጋገዝን የሚሰብኩ ናቸው ፡፡

በአብዘኛው የአፍሪካ ሀገራት በቅኝ አገዛዝ መዳፍ ውስጥ በነበሩት ወቅት ሀገራችን ኢትዮጵያ የካቲት 23 ቀን 1888 ዓ.ም የጣልያንን ወራሪ ጦር ያሸነፈችበት የአድዋ ድል 119ኛ ዓመትን ምክንያት በማድረግ በድሉ እንደሚኮራ እንደ አንድ ኢትዮጵያዊ በያገባኛል ስሜት ደክመን የሠራነው የአድዋ ድል መታሰቢያ ፕሮግራም በተፈቀደልን ቀንና የአየር ሰዓት እሁድ የካቲት 29 ቀን 2007 ዓ.ም ከሁለት ሰዓት እስከ ሶስት ሰአት እንዳይተላለፍ ተደረጎብናል ፡፡ይህ ያልተለመደ ነገር ሲከሰት ብናዝንም ቀደም ሲል የነበረንን መልካም የሥራ ግኑኙነት ከግምት ውስጥ በማስገባትና ወደፊትም እንደማይደገም በማመን ነገሩን በትዕግስት አልፈን አብረን ለመስራት ሞክረን ነበር፡፡

ይህ መፈጠሩ እያሳዘነን እያለ ሌላ ነገር ተከሰተ፡፡ ድርጅታችን በጣቢያቸሁ ፕሮግራም ማስተላለፍ ከጀመረበት ጊዜ ጀምሮ በተለይ በሀይማኖታዊና በዘመን መለወጫ በዓላት ላይ በተለያየ ጊዜና ሙያ ሀገራቸውን ያገለገሉ ግን ደግሞ የተዘነጉ የሀገር ባለውለታዎችን መጠየቅና የተቻለውን ያህል ድጋፍ ማድረግ የተለመደ ነበር፡፡በእዚህም መሰረት የ2007 ዓ.ም የትንሣኤን በዓልን ምክንያት በማድረግ ያዘጋጀነው ፕሮግራም በቂና አሳማኝ ባልሆነ ምክንያት እንዳይተላለፍ ተደርጎብናል፡፡
jossy gebre
ፕሮግራማችን በተደጋጋሚ በተለመደው የአየር ሰዓት እንዳይተላለፍ መደረጉ እያሳዘነን እያለ ፤በየመን ፤በደቡብ አፍሪካ በተለይም በሊቢያ አይ.ኤስ የተባለው ፅንፈኛ ቡድን በንጹሃን ዜጎቻችን ላይ ያደረሰውን ጥቃት ተከትሎ እንደ ኢትዮጵያዊ አዝነን ፤ቤተሰቦቻቸውን እና ዘመዶቻቸውን በሞት ከተነጠቁ ሀዘንተኞች ጎን ሆነን ሀዘናችን ገልጸንና የሀዘናቸው ተካፋይ ሆነን ድጋፍም አድርገን በተጨማሪም በኢትዮጵያዊ አንድነት ፤በሀይማኖት እኩልነት ፤ተፈቃቅሮ ፤ተቻችሎና ተከባብሮ በመኖር፤ እርስ በእርስ በመረዳዳት እንዲሁም ዜጎቻችንን ለእንግልትና ለሕልፈተ ሕይወት እየዳረገ ባለው ሕገ ወጥ ስደትና ሕገ ወጥ ደላሎች ዙሪያ ደክመን የሰራነው አስተማሪ ፕሮግራም ከጣቢያው በወሰድነው የአየር ሰዓት ላይ በተደጋጋሚ እንዳይተላለፍ መደረጉ ወደፊት አብሮ የመስራታችንን ነገር በጥርጣሬ እንድንመለከተው አድርጎናል ፡፡

ፕሮግራማችን በጣቢያችሁ ላይ መቅረብ ከጀመረበት ጊዜ ጀምሮ ለነበረን መልካም ግንኙነት ከልብ እናመሰግናለን፡፡ ከላይ ከጠቀስናቸው ችግሮች በተጨማሪ ሌሎችም ምክንያቶች ቢኖሩም የስራ ግኑኝነታችን እንዲቀጥል ስምምነት ለማድረግ ብንሞክርም አልተሳካም ፡፡ በእናንተ በኩል እየተከናወነ ያለው ያልተለመደ ተግባር የስራ ግኑኝነታችን እንዲቋረጥ ከፍተኛ ፍላጎት ያለ እንደሆነ እንድናምን ስላደረገን በእኛም በኩል ይህንን በአጽንኦት እንድንመለከተው አስገድዶናል፡፡

ከእዚህ በተጨማሪ ውል ተፈራርመን መስራት ሲገባን በድርጅታቸሁ አሰራር መሰረት ያለፈውን አንድ ዓመት ያለ ውል መስራታችን ይታወቃል ፡፡ ከአሁን በኋላ ግን በእዚህ አሰራር መቀጠል አንችልም ፡፡ ስለሆነም ከስፖንሰሮቻችን ጋር እስከ ሲዝን 4 የመጨረሻ 13ኛ ክፍል ድረስ የተደረገውን ውል ከግምት ውስጥ በማስገባት እስከ ግንቦት 30 ቀን 2007 ዓ.ም ድረስ ፕሮግራማችን በጣቢያቸሁ እንዲተላለፍ በእኛ በኩል አስቀድመን ዝግጅታችንን የጨረስን መሆናችንን እያሳወቅን፤ ከግንቦት 30 ቀን 2007 ዓ.ም ጀምሮ በጣቢያቸሁ ሲተላለፍ የነበረው “ጆሲ ኢን ዘ ሃውስ ሾው” የተሰኘው ፕሮግራማችን በእናተው አስገዳጅነትና ተገቢ ያልሆነ አሰራር እንደምናቋርጥ አስቀድመን እናሳውቃለን ፡፡
ከሰላምታጋር

The post ጆሲ ኢንዘሓውስ ሾው ለኢቢኤስ ቴሌቪዥን ማስጠንቀቂያ ጻፈ “ከግንቦት 30 ጀምሮ በእናንተ አስገዳጅነት ፕሮግራማችንን እናቋርጣለን” appeared first on Zehabesha Amharic.

የህወሓት አየር ኃይል ወደ ደቡብ ሱዳን የሚያደርገው ጉዞ መሰረዙ ተሰማ

0
0

ethiopian airforce
ምኒልክ ሳልሳዊ ዘንደዘገበው

የህወሓት አየር ኃይል ለሰላም ማስከበር ተልዕኮ ወደ ደቡብ ሱዳን የሚያደርገው ጉዞ መሰረዙ ተሰማ፡፡በበረራ፣ ጥገና፣ ድጋፍ ሰጪ፣ ዘመቻና አስተዳደር ከ200 በላይ አባላቱን በከፍተኛ ወጪ ለ6 ወራት ሲያሰለጥን የባጀው አየር ኃይል የሰላም ማስከበሩ ተልዕኮ ወደሚከናወንበት ደቡብ ሱዳን ሊጓዙ የተመረጡት መንገደኞች ከየአየር ምድቦቻቸው ተነስተው ደብረ ዘይት ከከተቱ በኋላ ጉዞው ድንገት ተዘርዟል፡፡

ጉዞው የተሰረዘባቸው ምክንያቶች በአባላትና አባላት፣ በአባላትና አመራሮች እንዲሁመም በአመራሮችና አመራሮች መካከል አለመተማመን በመስፈኑ፤ ያለመጠን ስር ሰዶ የተንሰራፋው ጎሰኝነት ተባብሶ በትግርኛ ተናጋሪ የህወሓት ሰዎች መካከልም ውቅሮና አዲግራት ወደሚሉ የመንደር ቡድንተኝነት ቁልቁለቶች በመውረዱ፤ ልክ እንደከዚህ ቀደሙ አሁንም አብራሪዎች ተዋጊ ሄሊኮፕተሮችን ይዘው ሊኮበልሉ ይችላሉ ከሚል ስጋት በመነጨ፣ ከፍተኛ በሆነ የአቅም ማነስ ችግር፤ ከምርጫው ጋር በተያያዘና ብረት ያነሱ የነፃነት ኃይሎች ጦርነት ይከፍታሉ ተብሎ በመሰጋቱ የሚሉት ዋና ዋናዎቹ ናቸው፡፡

በህወሓት ቁጥጥር ስር የሚገኘው አየር ኃይል ከዚህ በፊት በ2005 ዓ.ም በብቃት ማነስ ምክንያት ከዳርፉር ተባሮ የሰላም ማስከበር ተልዕኮውን ሳያሳካ ጓዙን ጠቅልሎ ውርደት በመከናነብ መመለሱ አይዘነጋም፡፡

The post የህወሓት አየር ኃይል ወደ ደቡብ ሱዳን የሚያደርገው ጉዞ መሰረዙ ተሰማ appeared first on Zehabesha Amharic.


በሚኒሶታ ለጊዜው ባልተረጋገጠ ሁኔታ ተገድሎ የተገኘው ኢትዮጵያዊ የቀብር ሥነሥርዓት ሊፈጸም ነው

0
0

abyu tekestebirhan
አብዩ ተከሥተብርሃን ይባላል:: ኤፕሪል 16 (ሚያዝያ 20 ቀን 2007 ዓ.ም) ከሥራ ውሎ ከተመለሰ በኋላ ከቤት እንደወጣ ሳይመለስ ስለቀረ ምን እንደደረሰበት ሳይታወቅ ሲፈለግ ሰንብቶ ከሁለት ሳምንታት በኋላ ለጊዜው ባልተረጋገጠ ሁኔታ ተገድሎ እንደተገኘ ቤተሰቦቹ ለቀብር ካዘጋጁት በራሪ ወረቀት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል:: መረጃው እንደሚለው ይህ ወጣት ኢትዮጵያዊ በሚኒሶታ እንዴት እንደሞተ ፖሊስ እያጣራ ያለበት ሁኔታ ሲሆን የቀብር ስነስርዓቱም የፊታችን ሜይ 22 (ግንቦት 20 ቀን 2007) ይፈጸማል::

በሚኒሶታና አካባቢው የምትገኙ ኢትዮጵያውያንና የኢትዮጵያውያን ወዳጆች በአሳዛኝ ሁኔታ ተገድሎ የተገኘውን ወጣት ወንድማችን ቀብር ስነሥርዓት ላይ እንድትገኙ ጥሪ ቀርቦላችኋል::

ሜይ 22 በሚኒሶታው ቅዱስ ዑራኤል ቤተክርስቲያን ከቀኑ 12:15 ጀምሮ የፍትሃት ስነስር ዓት የሚደረግ ሲሆን 2:45 ላይ ደግሞ በሜንዶታ ሃይትስ የመቃብር ሥፍራ ሥር ዓተ ቀብሩ ይፈጸማል:: አድራሻውም 2101 Lexington Ave S, Mendota Heights, MN 55120. ነው::

The post በሚኒሶታ ለጊዜው ባልተረጋገጠ ሁኔታ ተገድሎ የተገኘው ኢትዮጵያዊ የቀብር ሥነሥርዓት ሊፈጸም ነው appeared first on Zehabesha Amharic.

በደቡብ አፍሪካ በሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ላይ ጥቃቱ በተደራጀ መንገድ መቀጠሉ ተሰማ

0
0

በደቡብ አፍሪካ በሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ላይ እየተፈጸመ የነበረው ጥቃት ጋብ ብሎ የነበረው ቢሆንም፣ በተደራጀ መንገድ እንደገና መጀመሩን በደቡብ አፍሪካ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ለሪፖርተር ገለጹ፡፡
south africa ethiopia
ለበርካታ አፍሪካውያን ሕይወት መጥፋትና ንብረት መውደም ምክንያት የሆነውን ‘ዜኖፎብያ’ (የዘረኝነት ጥቃት) የደቡብ አፍሪካ መንግሥት ካወገዘ በኋላ፣ ለተወሰኑ ጊዜያት ተቀዛቅዞ የነበረው ጥቃት እንደገና አገርሽቶ 14 የኢትዮጵያውያን ሱቆች በቀናት ውስጥ እንደተቃጠሉ፣ በደርባንና በአካባቢው የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ማኅበር ፕሬዚዳንት አቶ ኤፍሬም ተስፋዬ ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡ በቃጠሎ የሰው ሕይወት ባይጠፋም አንድ ኢትዮጵያዊ አቅሉን ስቶ ሆስፒታል መግባቱን አቶ ኤፍሬም ጠቁመዋል፡፡

ከወትሮው በተለየ ሁኔታ በደርባንና በአካባቢው ወይም ክዋዙሉ ናታል በሚባለው አውራጃ ከጥቂት ቀናት በፊት ለኢትዮጵያውያን የሱቅ ባለቤቶች የማስፈራሪያ ደብዳቤም እንደደረሳቸው ተናግረዋል፡፡ ለሪፖርተር በኢሜይል የደረሰው ደብዳቤ በአሥር ቀናት ውስጥ እስከ እሑድ ግንቦት 9 ቀን 2007 ዓ.ም. አካባቢውን ለቀው እንዲሄዱ፣ ያለበለዚያ ግን ሞት እንደሚጠብቃቸው የሚያትት ነው፡፡ በኢትዮጵያውያን ዘንድ በቅጽል ስማቸው ‹‹የኡምላዚ ነጋዴ ገዳዮች›› ተብለው የሚታወቁት እነዚህ ጥቃት ፈጻሚዎች የሞት ደብዳቤ መሆኑን በመንገር፣ ለኢትዮጵያዊያኑ እንደሰጧቸው አቶ ኤፍሬም አስረድተዋል፡፡

እንደ አቶ ኤፍሬም ማብራሪያ፣ ጥቃቶቹ ድንገት ሳይሆን ለዓመታት ሲንከባለሉ የመጡ ናቸው፡፡ ‹‹በብዙ ሚዲያዎች ያልተነገረው በመጋቢት ወር አካባቢ የደረሰው የአምስት ኢትዮጵያውያን ተቃጥሎ መሞትም የዚህ ማሳያ ነው፤›› ያሉት አቶ ኤፍሬም፣ የቅርብ ጊዜው ጥቃት በደቡብ አፍሪካ መንግሥትና በዓለም አቀፍ ጫና ለጥቂት ቀናትም ጋብ ብሎ እንደነበር አስታውሰዋል፡፡ ለዓመታት ለፍተው ያፈሩት ንብረታቸውን ያጡ በርካታ ኢትዮጵያውያን ወደ ከተሞች በመሸሽና ከዘመድ ተጠግተው በመኖር ላይ እንደሆኑም ጠቁመዋል፡፡ አንዳንዶች ያላቸውን ንብረት በመያዝ ሱቆቻቸው እንደገና ለመክፈት ጥረት በማድረግ ላይ ቢሆኑም፣ ብዙዎቹ ሱቆች (ኮንቴይነሮችን) ጨምሮ በደቡብ አፍሪካውያን መወረሳቸውንም ይገልጻሉ፡፡

በቀን ይደረግ የነበረው ተቀይሮ ጥቃት ፈጻሚዎች ሱቆችን በምሽት በእሳት እያቃጠሉ መሆናቸውን ያስረዳሉ፡፡ ግንቦት 7 ቀን 2007 ዓ.ም. የአቶ ኤፍሬምን ጨምሮ አምስት ሱቆች መቃጠላቸውን፣ አቶ ኤፍሬም ግሮሠሪያቸው በመቃጠሉ ምክንያት 400 ሺሕ ብር ያህል እንዳጡ ተናግረዋል፡፡ ዘረፋዎችም እየጨመሩ እንደሆኑ ጠቁመዋል፡፡ ኢትዮጵያውያንን የሚኖሩበት ቦታ በመሄድ ማስፈራራቱም እንደቀጠለ ይናገራሉ፡፡ በሚያዝያ ወር አካባቢ በነበረው ጥቃት ምክንያት 15 ያህል ሰዎች በቁጥጥር ሥር ቢውሉም፣ በዋስትና መውጣታቸውን አቶ ኤፍሬም ይናገራሉ፡፡ በዚህም ምክንያት ኢትዮጵያውያን ለፖሊስ የከሰሱ ሲሆን፣ ጉዳያቸውም እየታየ እንደሆነ ይገልጻሉ፡፡ በቅርብ የተቃጠሉ ሱቆች 40 ያህል መሆናቸውን አሁን ደግሞ ከ50 መብለጣቸውን ያስረዳሉ፡፡ በሱቆች መቃጠልና በዘረፋው ምክንያት ከ800 እስከ 1,000 የሚገመቱ ኢትዮጵያውያን እንደተጐዱም ያክላሉ፡፡

በአካባቢው የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን 6,000 ያህል ይገመታሉ የሚሉት አቶ ኤፍሬም፣ ሁኔታዎች በዚህ ከቀጠሉ ለብዙ ኢትዮጵያውያን ደም መፋሰስ ምክንያት ሊሆን እንደሚችሉም ያስረዳሉ፡፡ ‹‹የነበረው ጥቃት ጋብ ያለ ቢመስልም ተዳፈነ እንጂ አልጠፋም፡፡ አሁንም እሳቱ እንደተቀጣጠለ ነው፡፡ በዚህ ከቀጠለም የኢትዮጵያውያን ደም እንደሚፈስ ምንም ጥርጥር የለውም፤›› ብለዋል፡፡

ኢትዮጵያዊያኑ ሥራ መጀመርና ከደቡብ አፍሪካውያን ጋር አብሮ በሰላም መሥራት እንደሚፈልጉ የሚናገሩት አቶ ኤፍሬም፣ ይህ ግን የማይቻል እንደሆነም ግምታቸውን ይናገራሉ፡፡ ቢሆንም ግን ሕይወታቸው አደጋ ውስጥ ሆኖም ብዙዎች ወደ ሥራ ለመመለስ በመጓጓት ላይ መሆናቸውን ይገልጻሉ፡፡ ‹‹ንብረቱን የተቀማና የተቃጠለበት ስደተኛ ብዙ ነገር ያጣ ቢሆንም፣ አሁንም ወደ ሱቁ መሄድን መርጧል፤›› በማለት ያለውን አስቸጋሪ ሁኔታ ጠቁመዋል፡፡

የኢትዮጵያ ኤምባሲ የዙሉን ንጉሥ ጉድዊል ዝዌልቲንና ቤተሰቦቻቸውን፣ እንዲሁም ሌሎች የደቡብ አፍሪካ ባለሥልጣናትን በማናገር ጉዳዩን ለመፍታት እየጣረ ቢሆንም ሁኔታው ግን አስቸጋሪ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

በሚያዝያው ጥቃት ምክንያት የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር 30 ያህል ኢትዮጵያውያንን ለመመለስ ችሏል፡፡ በአጠቃላይ ከ100 የሚበልጡ ኢትዮጵያውያን የተመዘገቡ ሲሆን፣ የመጀመሪያዎቹ ተመላሾች በቅርቡ አዲስ አበባ ገብተዋል፡፡ በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የመንግሥት ቃል አቀባይ አቶ ተወልደ ሙሉጌታ እንደሚሉት፣ ደቡብ አፍሪካ የሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ ደቡብ በአፍሪካ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ችግር እንዲፈታ ጥረት እያደረገ ነው፡፡ አሁን ደረሰ የተባለውን ጥቃት በተመለከተ ግን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ እንደሌለው አቶ ተወልደ ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡

የመመለሱን ሥራ የኢትዮጵያ መንግሥት የጀመረው ቢሆንም፣ በርካታ ኢትዮጵያውያን ግን ከሞት ጋር መጋፈጥን መምረጣቸው ታውቋል፡፡ መፍትሔው ምን ይሆን? ለሚለው አቶ ኤፍሬም ሲመልሱ፣ ‹‹የደቡብ አፍሪካ መንግሥትና ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ በዚህ ጉዳይ ጣልቃ ገብተው ጠንካራ ዕርምጃ እንዲወሰድ መደረግ አለበት፤›› ብለዋል፡፡

አሁን ደረሰ የተባለውን ጥቃት አስመልክቶ በደቡብ አፍሪካ የኢትዮጵያ አምባሳደር አቶ ሙሉጌታ ከልልን በስልክ ለማግኘት ጥረት ቢደረግም ሊሳካ አልተቻለም፡፡

Source: Ethiopian Reporter

The post በደቡብ አፍሪካ በሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ላይ ጥቃቱ በተደራጀ መንገድ መቀጠሉ ተሰማ appeared first on Zehabesha Amharic.

ዝነኛው አርቲስት ሠይፈ አረአያ አረፈ

0
0

seyfe areaya
(ዘ-ሐበሻ) የቢትዮጵያ ትያትር እና ፊልም ኢንዱስትሪ ውስጥ ትልቁን ድርሻ ያበረከተው አንጋፋው አርቲስት ሠይፈ አረአያ ከዚህ ዓለም በሞት ተለየ::

የዘ-ሐበሻ የአዲስ አበባ ዘጋቢዎች እንዳሉት ዝነኛው አርቲስት ለረጅም ጊዜ በህክምና ሲረዳ ቆይቶ በመጨረሻም ይህችን ምድር ተሰናብቷታል:: ብራቸውም ነገ በጉርድ ሾላ ሳሊተምህረት ቤተክርቲያን ይፈፀማል።

በብሄራዊ ትያትር እና በሌሎችም ትያትር ቤቶች በማገልገል በርከታ የመድረክ ሥራዎችን ያቀረበው ሰይፈ አረአያ በተለያዩ የአማርኛ ፊልሞችም ላይም ድንቅ ብቃቱን አሳይቷል::

ዘ-ሐበሻ በአርቲስቱ ሕልፈት የተሰማትን ጥልቅ ሃዘን እየገለጸች ለቤተሰቦቹ እና ለአድናቂዎቹ መጽናናትን እንመኛለን::

The post ዝነኛው አርቲስት ሠይፈ አረአያ አረፈ appeared first on Zehabesha Amharic.

በእነ ብርሃኑ ተ/ያሬድ ላይ የተመሰረተው ክስ ተሰማ * ‘ኤርትራን ተሻግራችሁ ግንቦት 7ን ልትቀላቀሉ ነበር’ተብለው ተከሰዋል

0
0

birhanu tekle

•‹‹በይልቃል ጌትነት እና በዮናታን ተስፋዬ ላይ መስክር እያሉ ያሰቃዩኛል›› ብርሃኑ ተ/ያሬድ
በነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተር
የፌደራል አቃቤ ህግ በቀን ሚያዝያ 22/2007 ዓ.ም በእነ ብርሃኑ ተክለያሬድ ላይ የመሰረተው ክስ ከሦስት ሳምንታት በኋላ ዛሬ ግንቦት 12/2007 ዓ.ም በልደታ ከፍተኛ ፍርድ ቤት 19ኛ ወንጀል ችሎት በንባብ ተሰምቷል፡፡
በብርሃኑ ተ/ያሬድ ስም በተከፈተው የክስ መዝገብ ላይ አራት ሰዎች የተካተቱ ሲሆን፣ እነዚህም 1ኛ ብርሃኑ ተ/ያሬድ፣ 2ኛ እየሩሳሌም ተስፋው፣ 3ኛ ፍቅረማርያም አስማማው እና 4ኛ ደሴ ካህሳይ ናቸው፡፡ የሽብር ክስ የቀረበባቸው እነዚህ ተከሳሾች በ1996 ዓ.ም የወጣውን የወንጀል ህግ (አንቀጽ 32(1)(ሀ) እና የጸረ ሽብር አዋጁ አንቀጽ 7(1)ን በመተላለፍ ወንጀል እንደተከሰሱ የክስ ቻርጁ ያመለክታል፡፡

በክሱ ላይ እንደተመለከተው ተከሳሾች ኤርትራ ውስጥ መቀመጫውን ባደረገውና በሽብርተኝነት በተፈረጀው ግንቦት ሰባት ስር አባል ሆነው የሽብር ተልዕኮ ለመፈጸምና ለማስፈጸም ወስነው ከድርጅቱ ጋር ለመቀላቀል የኢትዮጵያንና የኤርትራን ድንበር አቋርጠው ሊሻገሩ ሲሉ በቁጥጥር ስር የዋሉ በመሆናቸው በሽብርተኛ ድርጅት ውስጥ በአባልነት መሳተፍ ወንጀል ክስ ተመስርቶባቸዋል፡፡

ተከሳሾቹ ክሱን ካዳመጡ በኋላ ጠበቃ ማቆምን በተመለከተ ከፍርድ ቤቱ ለተነሳላቸው ጥያቄ ሁሉም ተከሳሾች፣ ‹‹ከተያዝን ጊዜ ጀምሮ በደል እየደረሰብን ነው፤ ይህ የብቀላ ስራ ነው ብለን ስለምናምን እና በዚህ ሁኔታ ተከራክረን ፍትህ እናገኛለን ብለን ስለማናምን የግልም ሆነ የመንግስት ጠበቃ አንፈልግም›› ብለዋል፡፡ ፍርድ ቤቱም ጠበቃ አለማቆም መብታቸው እንደሆነ በማውሳት ሀሳባቸውን የሚቀይሩ ከሆነ ጥያቄያቸውን ለመቀበል ዝግጁ ነው ሲል ገልጾዋል፡፡

በሌላ በኩል አንደኛ ተከሳሽ አቶ ብርሃኑ ተ/ያሬድ ለፍርድ ቤቱ ባሰማው አቤቱታ እንደገለጸው አሁን በሚገኝበት ቂሊንጦ ማቆያ ውስጥ በደል እየደረሰበት ይገኛል፡፡ ‹‹የተከሰስኩበት ወንጀል በክሱ ላይ የተመለከተው ሆኖ እያለ በግድ ቀድሞ እሰራበት በነበረው ሰማያዊ ፓርቲ ጓደኞቼ ላይ በተለይም በፓርቲው ሊቀመንበር ኢ/ር ይልቃል ጌትነት እና በህዝብ ግንኙነት ኃላፊው አቶ ዮናታን ተስፋዬ ላይ የግንቦት ሰባት አባል እንደሆኑ ተደርጎ መስክር እየተባልኩ ስቃይ እየደረሰብኝ ነው›› በማለት አቤቱታውን ያሰማው አቶ ብርሃኑ፣ በተጨማሪም ማንነትን መሰረት ያደረገ ስድብ እንደሚሰደብ፣ ጨለማ ቤት እንደሚታሰር እንዲሁም የተጠየቀውን ካልፈጸመ ወደማዕከላዊ ሊመልሱት እንደሚችሉ እንደሚዝቱበት ለፍርድ ቤቱ አስረድቷል፡፡

ፍርድ ቤቱ በበኩሉ አቶ ብርሃኑ አለኝ ያለውን አቤቱታ በጽሑፍ እንዲያቀርብ በማሳሰብ፣ አቤቱታውን አይቶ የሚመለከተው አካል መልስ እንዲሰጥ እንደሚያደርግ ገልጾዋል፡፡ ፍርድ ቤቱ ተከሳሾች በክሱ ላይ መቃወሚያ ካላቸው ለመቀበል ለግንቦት 28/2007 ዓ.ም ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡

The post በእነ ብርሃኑ ተ/ያሬድ ላይ የተመሰረተው ክስ ተሰማ * ‘ኤርትራን ተሻግራችሁ ግንቦት 7ን ልትቀላቀሉ ነበር’ ተብለው ተከሰዋል appeared first on Zehabesha Amharic.

የአ/አበባ ሰንበት ት/ቤቶች ለቅ/ሲኖዶሱ ባቀረቧቸው ጥያቄዎች እንቅስቃሴያቸውን አጠናክረው ቀጥለዋል

0
0

ሐራ ዘተዋሕዶ

  • የሰንበት ት/ቤቶቹን አንድነት ለማገድ እና አመራሩን ለመበተን መታቀዱን ተቃውመዋል
  • በአጥቢያዎች የተቀናጀ ፀረ ሙስና እና ፀረ ኑፋቄ እንቅስቃሴ እንደሚካሔድ ተጠቁሟል
  • ‹‹የቤተ ክርስቲያን ተረካቢ እንጂ የበዓላት ማድመቂያ ብቻ ቄጤማ አይደለንም››/ወጣቶቹ/

(ሰንደቅ፤ ፲ኛ ዓመት ቁጥር ፭፻፮፤ ግንቦት ፲፪ ቀን ፳፻፯ ዓ.ም.)

aassd5

በምዝበራ ላይ የተሰማሩ አማሳኝ የገዳማት እና የአድባራት ሓላፊዎች የሀብት ምንጭ እንዲመረመር፣ ማስረጃ በቀረበባቸው የተሐድሶ መናፍቃንበሕገ ወጥ ሰባክያን እና ዘማርያን ላይ ርምጃ እንዲወሰድ እንዲኹም ሕገ ቤተ ክርስቲያንን የሚጥሱ አካሔዶች እንዲታረሙና የቅዱስ ሲኖዶሱ ውሳኔዎች ተፈጻሚ እንዲኾኑ ያቀረቧቸው ጥያቄዎች ተገቢ ምላሽ እስኪያገኙ ድረስ እንቅስቃሴያቸውን አጠናክረው እንደሚቀጥሉ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት አብያተ ክርስቲያናት ሰንበት ት/ቤቶች ገለጹ፡፡

የርክበ ካህናት ቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ የመክፈቻ ጸሎት ሥነ ሥርዐት በመንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም ገዳም በተካሔደበት ዕለት፣ ዕቅበተ እምነትንና መልካም አስተዳደርን የተመለከቱ አምስት ዐበይት ጥያቄዎችን ለፓትርያርኩ እና ለቅዱስ ሲኖዶስ አባላት ማቅረባቸውን ሰንበት ት/ቤቶቹ አስታውሰዋል፡፡

ከ160 በላይ የአጥቢያ አብያተ ክርስቲያናት ሰንበት ት/ቤቶች የተውጣጡ ሦስት፣ ሦስት ሊቃነ መናብርት የተሳተፉበት የግማሽ ቀን ውይይት ባለፈው ሳምንት ቅዳሜ በሀገረ ስብከቱ ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት መሪነት የተካሔደ ሲኾን ጥያቄዎቹ የተስተናገዱበትን ኹኔታ በመገምገም ቀጣይ የእንቅስቃሴ አቅጣጫዎች መቀመጣቸው ተገልጧል፡፡

ከተለመደው በተለየ በአራት ቀናት በተጠናቀቀው የቅዱስ ሲኖዶሱ ስብሰባ ጥያቄዎቻቸው እንደተጠበቀው በአጀንዳ ተይዘው ውሳኔ አለማግኘታቸው እንዳሳዘናቸው በውይይታቸው የገለጹት ሰንበት ት/ቤቶቹ፣ የቤተ ክርስቲያኒቱን ቅድስና እና ሀብት የማስጠበቅ ትውልዳዊ ግዴታቸውን አስፈላጊ እና ሕጋዊ ርምጃዎችን በሙሉ በመጠቀም እንደሚቀጥሉበት አስታውቀዋል፡፡

Addis Ababa Sunday Schools at the Holy Synod Opening Prayer
ጥያቄዎቻቸው፣ በቃለ ዐዋዲው እና በሰንበት ት/ቤቶች አንድነት መተዳደርያ ደንብ አግባብ መቅረባቸውን ሰንበት ት/ቤቶቹ አረጋግጠው÷በመደጋገፍ እና በመተባበር ላይ በተመሠረተው የሀገረ ስብከቱ የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት መርሕ መሠረት በሰባት ክፍላተ ከተማ(ወረዳዎች) የተዋቀረው 69 አባላት ያሉት ሥራ አስፈጻሚ እና 11 አባላት ያሉት የሀገረ ስብከቱ አመራር ከሚመለከታቸው የቤተ ክህነት፣ የመንግሥት እንዲኹም ኅብረተሰብ አካላት ጋራ እየተገናኘ ተከታትሎ እንዲያስፈጽም መስማማታቸውን አስታውቀዋል፡፡

ሰንበት ት/ቤቶቹ÷ በቅዱስ ሲኖዶሱ የምልዓተ ጉባኤ ስብሰባ መክፈቻ ባቀረቧቸው ጥያቄዎች እና ወጣቱ ባሳየው ፀረ ኑፋቄ እና ፀረ ሙስና መነሣሣት ተደናግጧል ያሉት ‹‹አማሳኝ ቡድን››፣ ከአንዳንድ የሀገረ ስብከቱ እና የቤተ ክህነቱ ሓላፊዎች ጋራ በማበር የሀገረ ስብከቱን የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት አመራር አባላት ለማስፈራራት እና ለማሳሰር ሙከራ ማድረጉን ጠቅሰዋል፤ ከዚኽም አልፎ ከመጪው ጥቅምት የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ በፊት የሀገረ ስብከቱንና የክፍላተ ከተማ አመራሩን ከሓላፊነቱ ለማገድና በሀገረ ስብከቱ ጽ/ቤት የሚገኘውን ቢሮውን ለማሸግ መታቀዱ የሰንበት ት/ቤቶቹ ከፍተኛ ቁጣ እና ተቃውሞ የተገለጸበት እንደነበር ተናግረዋል፡፡

የቤተ ክርስቲያኒቱ እምነት፣ ሥርዐት እና ትውፊት ተጠብቆ ከትውልድ ወደ ትውልድ እንዲተላለፍ የማድረግ እና የቅዱስ ሲኖዶስ መመሪያዎችን የማስፈጸም ጥያቄዎቻቸው፣ ደንባዊ ብቻ ሳይኾኑ ፓትርያርኩ በቃለ ምዕዳኖቻቸው ያወጁት የብዙኃኑ አገልጋይ እና ምእመን ሮሮዎች መኾናቸውን ሰንበት ት/ቤቶቹ ይናገራሉ፡፡ ለቅዱስ ሲኖዶሱ ለማቅረብ የተገደዱትም ‹‹በየደረጃው ያሉ ሓላፊዎችም መፍትሔ ለመስጠት የሚቸገሩ መኾናቸውን በየጊዜው ባደረግናቸው ጥረቶች ያረጋገጥን በመኾኑ ነው፤›› ብለዋል፡፡

aassdሰንበት ት/ቤቶች፣ ‹‹የቤተ ክርስቲያኒቱን አስተዳደራዊ እና መንፈሳዊ አገልግሎት የሚረከብ በሥነ ምግባር የታነፀ ብቁ ትውልድ የሚፈሩበት የትምህርት እና የልማት ማእከላት እንጂ የበዓላት ማድመቂያ ቄጤማ ብቻ ተደርገን መታየት የለብንም፤››ያሉት ተወያዮቹ፣ ፓትርያርኩ የብዙኃን አባት እንደመኾናቸው በልጅነታችን ጠርተው ሊያወያዩን ይገባ ነበር በሚል የተሰማቸውን ቅሬታ ገልጸዋል፡፡

እንደሰንበት ት/ቤቶቹ ገለጻ፣ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ አጥፊው የሚሾምበት፣ መልካም ሠሪው የሚታገድበት የጎጠኝነትና የጥቅመኝነት አሠራሮች መንሰራፋታቸው ለአገልግሎት ትልቅ ዕንቅፋት ፈጥሮአል፡፡ አኗኗራቸው ከደመወዛቸው የማይመጣጠን ጥቂት የማይባሉ ሓላፊዎችና ሠራተኞች ከግብር አበሮቻቸው ጋራ በመኾን ቤተ ክርስቲያኗን ሰላም እየነሱ ነው፡፡ በምትኩ በየአጥቢያው ሙስናንና ኑፋቄን የሚያጋልጡ የሰንበት ት/ቤት ወጣቶች ‹‹ሽብርተኞች ናቸው፤ መንግሥትን ለመገልበጥ አሲረዋል›› በሚሉ ሰንካላ ምክንያቶች እየተዋከቡ ነው፡፡

የሀብታም ልጆችና የድኻ ልጆች ብለው ከፋፍለው ትምህርተ ሃይማኖት እናስተምራለን የሚሉ ግለሰቦችና ሓላፊዎች እንዲታረሙ የቀረቡት አቤቱታዎች ሰሚ ጆሮ አላገኙም፡፡ ኹኔታው የቤተ ክርስቲያኗን አስተምህሮ የሚፃረሩና ማስረጃ ቀርቦባቸው ጉዳያቸው በእንጥልጥል የተያዘ ግለሰቦች ሳይቀር ስማቸውን ቀይረው በመዋቅሯ ውስጥ በመስረግ በጥፋት ተልእኳቸው ለመግፋት ምቹ ኹኔታ ፈጥሮላቸዋል፡፡ በአጠቃላይ ፓትርያርኩ ሙስናንና ብልሹ አሠራርን ከቤተ ክርስቲያን በማጥፋት ቅድስናዋን፣ ልዕልናዋንና ክብርዋን እንደሚያስመልሱ በተደጋጋሚ የገለጡ ቢኾንም እስከ አኹን ምንም የታየ ለውጥ ባለመኖሩ ችግሩ እየከፋ አቤቱታዎች ተጠራቅመው አቅጣጫቸውን እንዳይስቱ ምላሽ እንዲሰጣቸው ሰንበት ት/ቤቶቹ ድምፃቸውን አሰምተው ይጠይቃሉ፡፡

‹‹ለቤተ ክርስቲያን ተልእኮ የማይመጥኑና ቅድስናዋን የሚፃረሩ አሳፋሪ ድርጊቶች አንገታችንን እያስደፉና እያሳፈሩን አይተን እንዳላየን፣ ሰምተን እንዳልሰማን ለማለፍ ሃይማኖታችንም ኾነ ሕሊናችን ስለማይፈቅድ፣ በእግዚአብሔር ዘንድ ስለሚያስጠይቁንና በታሪክም ስለሚያስወቅሱን ጩኸታችን ሰሚ እስኪያገኝና የሚታረምበት አሠራር እስኪዘረጋ ድረስ አማሳኞችን ከቢሮ ለማስወጣት፣ መናፍቃንን ከዐውደ ምሕረት ለማውረድ በየአጥቢያው መንቀሳቀሳችንን አጠናክረን እንቀጥላለን፤ በዚኽም የሚመጣውን መሥዋዕትነት እንቀበላለን እንጂ ቤተ ክርስቲያናችንን ለአማሳኞች እና ለተሐድሶ መናፍቃን አሳልፈን አንሰጥም፤›› ይላሉ፡፡

The post የአ/አበባ ሰንበት ት/ቤቶች ለቅ/ሲኖዶሱ ባቀረቧቸው ጥያቄዎች እንቅስቃሴያቸውን አጠናክረው ቀጥለዋል appeared first on Zehabesha Amharic.

የሕወሓት አስተዳደር በጦር መኮንኖች ላይ ከግንቦት 7 ጋር ልባችሁ ኮብልሏል በሚል ክስ መሠረተ

0
0

Zehabesha News
ከግንቦት ሰባት ድርጅት ጋር ግንኙነት ፈጥረዋል፤ አባላትን መልምለዋል፤ ለቡድኑ መረጃ አቀብለዋል፤ እንዲሁም ወደኤርትራ በመኮብለል የድርጅቱን ፖለቲካዊና ወታደራዊ ስልጠና ለመውሰድ ተሰናድተው ሲንቀሳቀሱ ደርሼባቸዋለሁ በሚል የፌዴራል ዐቃቤ ሕግ ክስ የመሰረተባቸው ሰባት የመከላከያ ሰራዊት አባላት ትናንት ግንቦት 11 ቀን 2007 ዓ.ም በፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት 19ኛ ወንጀል ችሎት ቀረቡ።

በአዲስ አበባ የሚታተመው ሰንደቅ ጋዜጣ እንደዘገበው “በዐቃቤ ሕግ ክስ የተመሰረተባቸው ተከሳሾች 1ኛ መቶ አለቃ ማስረሻ ስጤ፣ 2ኛ መቶ አለቃ ብሩክ አጥናዬ፣ 3ኛ መቶ አለቃ ዳንኤል ግርማ፣ 4ኛ መቶ አለቃ ገዛኸኝ ደረሰ፣ 5ኛ ተስፋዬ እሸቴ፣ 6ኛ ሰይፉ ግርማ እና 7ኛ የሻምበል አድማው አዳሙ ናቸው። እንደክስ ዝርዝሩ ከሆነ ተከሳሾቹ በዋና ወንጀል አድራጊነት ተካፋይ በመሆን በቀጥታ እንዲሁም በመላ ሃሳባቸውና አድራጎታቸው በወንጀል ድርጊቱና በሚሰጠው ውጤት ሙሉ ተካፋይ በመሆን ሕገ-መንግስቱን እና ሕገ-መንግስታዊ ስርዓቱን በኃይል የማፈራረስ ዓላማን ይዘው ለማስፈፀም እና በመንግስት ላይ ተፅዕኖ ለማሳደር፤ ህብረተሰቡን ለማስፈራራት፤ የአገሪቱን ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ተቋማት ለማናጋትና ለማፍረስ ከሚንቀሳቀሰውና በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሽብርተኛ ከተባለው የግንቦት ሰባት ድርጅት አባል በመሆንና በሽብር ድርጅት ለመሳተፍ ሲንቀሳቀሱ ደርሼባቸዋለሁ” ይላል።

የፌዴራሉ ዐቃቤ ሕግ ትናንት በችሎት ለተገኙት ተጠርጣሪዎች ክሱ እንደደረሳቸው ተደርጎ በዝርዝር ሲነበብ፤ በተጠርጣሪዎቹ ላይ 10 ክሶች እንደቀረቡባቸው ለማወቅ ተችሏል። በተለይም ከ1ኛ እስከ 6ኛ ተከሳሾች ላይ በቀረበው ክስ መሠረት ቀኑና ወሩ በትክክል ተለይቶ ባልታወቀበት በ2006 ዓ.ም ከሽብር ድርጅቱ ከፍተኛ አመራር ከሆነው ሻለቃ አክሊሉ መዘነ አማካኝነት በህቡዕ ተመልምለው አባላትን እንዲመለምሉም ተልዕኮ ተሰጥቷቸው ይንቀሳቀስ ነበር ሲል ያትታል። በመሆኑም ተጠርጣሪዎቹ እያንዳንዳቸው ከአፌዲሪ መከላከያ የአየር ኃይል ንብረት የሆኑ አንድ-አንድ ማካሮቭ ሽጉጥና 16 ጥይቶችን ይዘው በመውጣትና በመሸጥ፤ እያንዳንዱ አንዱን ማካሮቭ በ2ሺህ 500 ብር እንዲሁም እያንዳንዳቸው የያዙትን 16 ጥይቶች በ240 ብር ዋጋ በመሸጥ ለግል ጥቅማቸው በማዋል በፈፀሙት ወታደራዊ ትጥቅና መሣሪያዎችን ያለአግባብ መገልገል ወንጀል ተከሰዋል ባይነው፤ዐቃቤ ሕግ።

በመሆኑም ተጠርጣሪዎቹ በአጠቃላይ በሽብርተኛ ድርጅት ውስጥ አባል በመሆን፣ ተልዕኮ በመቀበል፣ አባላትን በመመልመል፣ ለሽብር ድርጅቱ መረጃ በማቀበል እንዲሁም የሽብር ድርጅቱን ለመቀላቀል ወደኤርትራ ለመሄድ ሲሉ የተያዙ በመሆናቸው በፈፀሙት በሽብርተኛ ድርጅት ውስጥ በማናቸውም መልኩ መሳተፍ ወንጀል ተከሰዋል ሲል የክስ መዝገቡ ያትታል።

በዐቃቤ ሕግ የክስ ዝርዝር ውስጥ በብቸኝነት 10ኛው ክስ የተመሰረተበት ሻንበል አድማው አዳሙ ፈፅሞታል የተባው ወንጀል ከኢፌዲሪ አየር ኃይል ድሬዳዋ ቅርንጫፍ የሆነ አንድ ማካሮቭ ሽጉጥ ከ8 ጥይቶች ጋር በ33 ሺህ 700 ብር መግዛቱ እንደሆነ የጠቀሰው የዐቃቤ ሕግ ክስ፤ በዚህም በፈፀመው በከባድ ሁኔታ የመሸሸግ ወንጀል ተከሷል ይላል።
ተከሳሾቹ ትናንት (ማክሰኞ ግንቦት 11 ቀን 2007 ዓ.ም) ችሎት በቀረቡበት ወቅት የዋስትና መብታቸው እንዲከበርላቸው የጠየቁ ሲሆን፤ ዐቃቤ ሕግ በበኩሉ የጠቀስኳቸው የወንጀል አንቀፆች የዋስትና መብትን የሚያስከለክሉ ናቸው በሚል ለችሎቱ በማስረዳቱ ተቀባይነት አግኝቷል። በመሆኑም ተከሳሾቹ በማረሚያ ቤት ሆነው ጉዳያቸውን እንዲከታተሉ ታዟል። ነገር ግን በ7ኛ ተከሳሽ ጉዳይ ላይ ያለውን የዋስትና ጥያቄ መርምሮ ብይን ለመስጠትና ሁሉም ተከሳሾች በቀረበባቸው ክስ ላይ ያላቸውን ሀሳብ ለማዳመጥ ለግንቦት 21 ቀን 2007 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ይዟል ሲል ሰንደቅ ጋዜጣ ዘግቧል::

The post የሕወሓት አስተዳደር በጦር መኮንኖች ላይ ከግንቦት 7 ጋር ልባችሁ ኮብልሏል በሚል ክስ መሠረተ appeared first on Zehabesha Amharic.

ግልጽ ደብዳቤ ለፕሬዘዳንት ባራክ ኦባማ ከየሸዋስ አሰፋ ቅሊንጦ

0
0

Yeshiwas
ክቡር ፕሬዘዳንት ለመጀመሪያ ጊዜ በቴሌቪዥን ያየሁዎትበፕሬዘዳንትነት ለመመረጥ በተወዳደሩባቸው ጊዜያት ሲሆን በወቅቱ ከእርስዎ ምርጫ ጋር በተገናኘ ድምጽ መስጠት ባልችልም ምርጫውንለመከታተል ብዙ ጊዜዬን እነዳሳለፍኩ አስታውሳለሁ፡፡ በወቅቱ ይህንንያደረኩት የተመረጡት ለአሜሪካን መሆኑን አጥቼው ሳይሆን የታላቅዋ አገር መሆንዎ በወቅቱ ከነበረው ተስፋ ጋር ተደምሮ ለአለም ሰላምሊያበረክቱ የሚችሉትን በጎ ምግባር ተስፋ በማድረግ ነበር ፡፡

አሁን ይህንን ደብዳቤ እንድጽፍልዎት ያነሳሳኝግን ዛሬ መንግሰትዎ የውጪ ጉዳይ መስሪያ ቤት ሰራተኛ እና የመስሪያ ቤቱ ከፍተኛ አመራር የሆኑት ምክትክ ሚኒስትሯ ዌንዲ ሸርማንአዲስ አበባ መጥተው የተናገሩት ንግግር ነው ፡፡ መቼም አንደሚገምቱትአንደማንኛውም ኢትዮጲያዊ ንግግራቸው ስሜቴን መርዞታል፡፡

ምክትል ሚኒስትሯ የተናገሩት ብዙ ጉዳይ ላይ ነው፡፡ ስለሽብርተኛነት ፣ ስለምስራቅ አፍሪካ ሰላም፣ ስለግንቦት 7 ስለ ኢትዬጵያ እድገት ሰላም ዴሞክራሲ ወዘተ፡፡ ዋና ጉዳይ ብለውየገለጹት የቀጣዩ የ2007 ምርጫ ላይ የሰጡት አስተያየት ግን እጅጉንአሳዝኖኛል፡፡ ምርጫው ከጊዜ ወደጊዜ እየተሻሻለ ነው መጪው ምርጫ ዴሞክራሲያዊ ፍትሃዊና ተአማኒነት ያለው እንደሚሆን አንጠብቃለን ነበር ያሉት፡፡ ይበልጥ የሚያሳዝነው ደግሞ ይህ የልእለ ሃያልዋ አሜሪካ አቋምመሆኑን መግለጻቸው ነው ፡፡ መቼም በፍቃደኝነት ካልሆነ በስተቀር ምንም አይነት አጭበርባሪ አምባገነን በዚህ ደረጃ ያጃጅላቸዋልብሎ ማመን ይከብዳል፡፡

ለዴሞክራሲያዊ ምርጫ የሚያስፈልጉ ቅድመ ሁኔታዎችበመዘርዘር ውድ ጊዜዎን አላጠፋም፡፡ ነገር ግን በኢትዮጵያ በየአምስት አመቱ ምርጫ በመጣ ቁጥር የሚሰሩና እየተሰሩ ያሉ ምርጫ አደናቃፌዎችንልገልጽልዎት እፈልጋለሁ፡፡ ከእነዚህ አደናቃፌዎች መካከል መጨውን ምርጫ 2007 ከመቼውም ጊዜ በላይ የከፋ የሚያደርጉት

1. ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ከመዋቅሩ ውጪ ባሉ ግለሰቦች የሚሽከረከር አቅመቢስ ተቋም ከመሆኑም ባሻገርዛሬ ገዥው ቡድን አንደራሱ የፓርቲ አካል የሚያሽከረከረው መሆኑ
2. ገዥው ቡድንም ምንም አይነትየፓርቲ ቅርጽ የሌለውና ከ20 አመታት በፌት ጀምሮ በአሜሪካን መንግሰት በአሸባሪነት ተፈርጆ የነበረው ህወሃት በጠርናፌነት ጠቅልሎየያዘውና ምርጫውንም የስልጣን ጊዜውን ለማራዘም ብቻ የሚጠቀምበትመሆኑ
3. ምርጫ በመጣ ቁጥር 1987ኦነግን ፣ በ1992 መአህድን፣ በ1997 ቅንጅትን ፣ በ2002 አንድነትን በ2007 ሰማያዊን ኢላማ በማድረግ የተሻሉ ተፎካካሪፓርቲዎቸን በማጥፋት አመራርና አባላቶቸን በማሰር ብቻውን የሚወዳደር መሆኑ
4. በፓርቲና በመንግሰት መካከልያለው ልዬነት ጭራሽ ጠፍቶ የፍትህ አካላትና ፍርድ ቤቶቸን ሳይቀር በቀጥታ የፓርቲ አገልጋዮች ያደረገ መሆኑ
5. ከመቼውም ጊዜ በባሰ ሁኔታዛሬ ኢትዮጵያ ውስጥ ምንም የግል ሚዲያ የሌለ መሆኑና 90 ሚሊዬን ህዝብ በሚኖርበት አገር 2000 ኮፒ የሚያሳትሙ ህትመቶችን ሳይቀርበመዝጋት ጋዜጠኞችና ጦማርያንን ወህኒ የከተተ መሆኑ
6. ከምርጫ 97 በኋላ በወጣውአፋኝ አዋጅ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ምንም አንዳይሰሩ ተደርገው ትውልዱ መሪ እና አስተማሪ ያጣ መሆኑ
7. ህገ መንግስቱ ን በጸረ ሽብርአዋጅ በመጣስ የተለያዬ የአገሪቱን ዜጎች በተለይ ኦሮሚኛ ተናጋሪ ኢትዮጲያውያንን በጅምላ ማሰር ፣ በሃይማኖት ጣልቃ መግባት በተለይየእስልምና ሃይማኖት ተከታይ ኢትዮጵያውያንን በጅምላ በማሰር እስርቤቶችን በፓለቲካ እስረኛ የሞላቸው በመሆኑ
8. በአገዛዙ በተለያዬ የስልጣንእርከን ያሉ ግለሰቦች ስልጣናቸውን መከታ በማድረግ ከልክ ያለፈ ገንዘብ እየመነዘሩና ሙስና ውስጥ የተዘፈቁ በመሆኑ እና ዛሬም በአልጠግብባይነት በዚሁ መቀጠል የሚፈልጉ መሆኑ
9. ምርጫ 2007 የአውሮፓ ህብረትንጨምሮ ሌሎች ተአማኒነት ያላቸውና አምባገነኖችን የማጋለትጥ ልምድ ያላቸው ድርጅቶች የማይታዘቡት መሆኑ ዋና ዋናዎቹ ናቸው፡፡

ፕሬዘዳንት ኦባማ-በዛሬዋ ኢትዮጵያ እነዚህ ችግሮች አይኑን ለጨፈነ አንኳን የሚዳሰሱ ሃቆች ሆነው ሳለ የመረጃ ሰዎችዎ ይስቷቸዋል ብዬ አላምንም፡፡ የገዥዎችፕሮፓጋንዳ ስክሪን ሴቨር ኑሮ የሚገለጸውን እውነታም የሚሸፍንባችሁ አይመስለኝም፡፡ ታዲያ ከላይ የተገለጹት መባባሶች መሻሻል ተብለውሲገለጹ አንድ ኢትዮጵያዊ ዜጋ ምን የሚሰማው ይመስልዎታል? ይህ የተገለጸው ደግሞ በዴሞክራሲ በተመረጠ መንግስትና መሪ ካለበት አገርሲሆንና ገዥው ቡድን ለሚደርገው ግፍና ጭቆና አሜሪካ እውቅና ስትሰጥስ ?

እነደሃያል አገር ሲሆንሲሆን የነጻነት ትግል ላይ ያሉ ህዝቦችን ማገዝ ሲገባ ፣ ማገዝ ካልተቻለም ደሞ ቁስላቸው ላይ ሚጥሚጣ ባለመጨመር ዝም ማለት አይቻልም?የአለምን ሰላም ካለነጻነት ማሰብ አንደማይቻል የተቀመጡበት የአባቶችዎም ዙፋን አንደሚያሳይዎት አውቃለሁ ታዲያ የህዝቦችን የነጻነት ትግል ማጣጣል ለምን ??

እርስዎም ሆኑ ሸርማንየአሜሪካንን ጥቅም አንደምታስቀድሙ እናውቃለን፡፡ መረሳት የሌለበት ቁም ነገር ግን ህዝባዊ ወዳጅነትን አንጂ አምባገነን አገዛዙንበመተማመን የሚገኘው ጥቅም ዘላቂ አለመሆኑ ነው፡። ከአገዛዞች ጋር የሚደረገው ቁማር አሜሪካን ቆምኩለት የምትለውን የሞራል ልእልናእና እሴት የሚመጥን አይመስለኝም፡፡ ቢያንስ በአገር ደረጃ ጥቅም ህሊናን ገርስሶ የፓለቲካ ትርፍ ሰው መሆንን ጨርሶ መደምሰስ የለበትም፡፡ትልቅነት የአለምን ሰላም መጠበቅ ከሚወሰድ ሃላፌነት ቀርቶ ሌላውን ለመዋጥ ለሚከፈት አፍ ከተለካ ህገ አራዊት የአለም ትልቁመተዳደሪያ ይሆናል፡፡

ፕሬዘዳንት ኦባማ-ለዴሞክራሲያዊ ስርአት አንጂ ለአምባገነንነት ጥሩ ፊት አንደማይኖርዎት እረዳለሁ፡፡ በአሁኑ መልእክት ግራ የተጋባሁትም ከዚህ የተነሳነው፡፡ አምባገነን የሚያስበው በአይኑ ነው እንደሚባለው የኢትዮጵያ አገዛዝ በአሁኑ ሰአት እውነት ቢነገረውም እንደማይሰማ ይታወቃል፡፡የወይዘሮዌንዲ ሸርማን መግለጫ ሊወድቅ ሳምንታት ሲቀሩት የግብጽ አገዛዝ “strong and stable government” ….. “ጠንካራ እና የተረጋጋ መንግስት” ከሚለው በወቅቱ የአሜሪካንየውጪ ጉዳይ ሚኒስተር ከነበሩት ወ/ሮ ሂላሪ ክሊንተን መግለጫ ጋር ተመሳሳይ ሆኖብኛል፡፡ ይህ አይነት ከእውነታው ያፈነገጠ አገላለጽለሁለቱም አገሮች አንደማይጠቅም ይገባዎታልም ብዬ ተስፋ አደርጋለሁ፡፡

ፕሬዘዳንት ኦባማ- የኢትዬጵያ ታላቅነት ይመለሳል፡፡ በእርግጥም በነጻነትና በዴሞክራሲ ምርጫ ወደስልጣን የሚወጣ ተርሙን ሲጨርስ ለቀጣዬ በሰላምየሚያስረክብ መሪ ይኖራታል፡፡ ህዝቦቿ በእርቅ ይተቃቀፋሉ፡፡ ጨቋኝም ተጨቋኝም ነጻ ይወጣሉ ፡፡ ኢትዬጵያ ጦር በመስበቅ ሳይሆንፍቅርን በተግባር በመስበክ ለአካባቢዋም ለአለምም አስተዋእጾ የምታበረክትበት ጊዜ ሩቅ አይሆንም ፡፡ ለዚህ ታላቅ ሽግግር እርሶምአንደመሪ አገርዎም እነደሃያል አገር ከኢትዮጲያ ጎን ብትቆሙ የሁለቱ አገሮች ጥቅም በአለት ላይ የተመሰረተ ይሆናል፡፡

ቀሪው የስራ ዘመንዎምይህን የአሜሪካን የሞራል ልእልና በተግባር የሚያሳዩበት አንዲሆን እመኝልዎታለሁ፡፡ ፈጣሪ ኢትዮጵያንም አሜሪካንንም ይባርክ፡፡

የሸዋስ አሰፋ! ከቅሊንጦኢትዮጵያ

The post ግልጽ ደብዳቤ ለፕሬዘዳንት ባራክ ኦባማ ከየሸዋስ አሰፋ ቅሊንጦ appeared first on Zehabesha Amharic.


መጀገን –በምርጫ ቀን

0
0

election
(ሀብታሙ ስዩም እንደ ጻፈው)

ከወረቀቱ አናት ላይ እንዲህ ተጽፏል፡፡‹‹ለመምረጥ በሚፈልጉት ፓርቲ ምልክት ፊት ለፊት የ ‹ኤክስ› ምልክት ያድርጉ፡፡››በወረቀቱላይ የተደረደሩ ፓርቲዎችን ስምና ምልክታቸውን በቀስታ ቃኘ፡፡በመጀመሪያው ረድፍ አመልካች ጣት፣ሁለት ጣት ፣አምስት ጣት ….በሌላኛውረድፍ ፈረስ፣ንብ፣አበባ …አየ፡፡

አገጩን ተደግፎ ፈገግ አለ፡፡ፊት ለፊት በሚተያዩት ምልክቶች መካከል ሳይቀር ፍጥጫያለ መሰለው፡፡አመልካቹ ጣት ሰጋሩን ፈረስ ቀጭን ትዕዛዝ ለመስጠት የተቀሰረ አይነት ነው፡፡ሁለት እግሮቹ አየር ላይ ሁለት እግሮቹምድር ላይ ያለው ፈረስ ደግሞ እንጃልህ እያለ እየጎፈላ ነው፡፡ ሁለቱ ጣቶች ንቧን ይዘው ሊያልዘምዟት የቋመጡ እንደሆኑ ያሳብቅባቸዋል፡፡ንቧ በሚጠጋ ጣት ላይ ነዝናዥ እሾኋን ለመቀብቀብ እንደ ቆረጠች አይነት ተነፋፍታለች፡፡አምስቱ ጣቶች አበባዋን ለመቀንጠስ የሆነ አጋጣሚ ብቻ የሚፈልጉ አይነት ናቸው፡፡የአበባዋ መዝመም በጣቶቹ ውስጥ ላለመግባት እንደመሸሽአይነት ሆነበት፡፡

‹‹ወንድሜ ቶሎ ምረጥና ቦታ ልቀቅ እንጂ ብዙ መራጮች እኮ እየጠበቁ ነው፡፡››የሚል ድምጽ በሚስጢር ድምጽ መስጫዋ ጠባብ ክፍል የጨርቅ ግድግዳ አልፎ ተሰማው፡፡ከያዘው የሃሳብ መዋለል ራሱን አነቃና እስኪርቢቶውንአቀባበለ፡፡

‹‹ማንን ልምረጥ?›› ለራሱ አንሾካሾከ፡፡እናቱ ትዝ አሉት፡፡የብዙ አማራጮች ንግስትየተለዩ ፍልስፍናዎች ግምጃ ቤት የሆኑት እናቱ ያወሩት መሰለው፡፡
‹‹እኔ በበኩሌ አባ ዮሴፍን ብትመርጣቸው ደስ ይለኛል፡፡››

‹ማናቸው አባ ዮሴፍ›
‹‹እኚህ ከዳቦ ቤቱ ጎን ባለው ቤት ውስጥ የሚኖሩት ሰውዬ ናቸዋ፡፡››
‹‹እንዴት ነው የትምህርት ደረጃቸው?››
‹‹መቸም ከአባዱላ አያንሱም››
‹‹ከህዝብ ጋር ለመጮህ ዝግጁ ናቸው?››
‹‹ሚሰማቸው ከተገኘ!››
‹‹ለምንድነው እሳቸውን እንድመርጥ የፈለግሽው?››
‹‹እንጃ እንዴው ሳያቸው አንጀቴን ይበሉኛል፡፡ጡሮታ ከወጡ በኃላ እንቅልፍ ያላቸውምአሉ፡፡››
‹‹እና ፓርላማ እንዲገቡ የምመርጣቸው እንዲንቀለፉ ነው?››
‹‹መቸም ከዚህ የተለየ ሲያደርግ ያየነው የፓርላማ አባል የለም፡፡››
አባዮሴፍን የማይመርጥበት ምክንያት ምልክታቸውን ሳላልወደደው ነው፡፡የአባ ዮሴፍየምርጫ ምልክት ሰባት ቁጥር ነው፡፡የመንግስት ደጋፊዎች ለምን ሰባት ቁጥርን ተጠቀምክ ሲሏቸው ‹‹ደደቢት በረሃ የገቡትን የመጀመሪያሰባት ታጋዮች ለማሰብ ነው ይላሉ፡፡የመንግስት ጠላቶችን በሚያገኙ ጊዜ ታሪኩን ይቀይሩታል ‹የጀግኖች ስብስብ የሆነውን ግንቦት7ን› ለማስታወስ ነው ብለው ይሸውዳሉ፡፡እንደ እማየ ያሉትን ከቤተመንግስት ይልቅ የቤተ ክርስቲየን ጉዳይ የሚመስጣቸውን ሰዎች ሲያገኙ ደግሞ‹ ወር በገባ በሰባት የሚውሉት ስላሶች ከጎኔ ናቸውለማለት ነው›› ብለው አንጀት ይበላሉ፡፡
እሱ ግን ሰባት ያለበት ነገር በጤና ተጠናቆ ስለማያውቅ አልራራላቸውም፡፡ማስረጃአቅርብ ቢባል 67ን ይጠቅሳል- ወጣት እንደ ስጦ አስፓልት የሸፈነበትንዓመት፡፡77ን ያነሳል- ርሃብ እንደ ቄጠማ ትውልድ የረመረመበት አመትን፡፡87ንያስታውሳል- አጎቱ ከነ መፈክሩ ስድስት ኪሎ በር ላይ የተደፋበትን፡፡97ን ይጠቅሳል – እሱና ወዳጆቹ ደዴሳ የከረሙበትን፡፡ዘንድሮደግሞ—-እንጃ እንግዲህ፡፡ብቻ ላይመርጣቸው ምሏል፡፡
አሁንም ወረቀቱ ላይ እንዳቀረቀረ ነው፡፡እስኪርቢቶውን በጣቶቹ መሃል ያሽከረክራል፡፡የምርጫአስተባባሪው ድምጽ በድጋሚ አባነነው፡፡
‹‹ኧረ ወንድሜ ፈጠን በልና ጨርስ፡፡ብዙ ሰው እኮ አንተን ነው የሚጠብቅ፡፡››
‹‹እሺ ትንሽ ታገሰኝ…››መልሶ የምርጫ ምልክቶችን ይመረምር ገባ፡፡
‹‹ማንን ልምረጥ ?›› የእናቱ ድምጽ በድጋሚ መጣበት፡፡

‹‹ኢህአዴግን ብትመርጥ ይሻላል፡፡››
‹አብደሻል?››
‹‹ባብድ በምን እድሌ ! ዘንድሮ እብድ እና ሰካራም ብቻ አይደል የልቡን እንዲናገርየተፈቀደለት›
‹‹ለምንድነው ኢህአዴግን የምመርጠው…?››

‹‹መረጥከውም አልመረጥከውም ጎረምሳው መንግስት ምርጫውን ማሸነፉ አይቀርም፡፡አንተባትመርጠው አንዳች ነገር አይጎድልበትም፡፡እንደሚባለው በየምርጫ ጣቢያው ስውር ካሜራ ካለው ደግሞ ይሄ ውሳኔህ ኮንደሚኒየም አልባ እና ምልምል ሽብርተኛ ያደርግሃል፡፡ለበለጠጦስ እራስን ከማመቻቸት ‹ደስ ይበላችሁ ያው መረጥኳችሁ ብሎ ማለፍ ይሻላል፡፡እነሱ እቴ ከስልጣን ወንበር ጋር አብረው ተሰፍተውእንኳን ህዝብ ቸሩ መድሃኒያለም ሰቅስቆ የሚያነሳቸውም አይመስሉም፡፡››
‹‹እማዬ ምርጫ ጣቢያ ውስጥ ካሜራ የለም፡፡››
‹‹አትሞኝ ልጄ፡፡በሁሉም ቦታ የስለላ መሳሪያ አላቸው ፡፡ሌላው ይቅር በስልክ ምትነጋገረውንሁሉ ጠልፈው ያዳምጣሉ፡፡ይሄን ያልኩት ካለ ማስረጃ አይደለም፡፡ባለፈው እንጀራ እየጋገርኩ ከማስረክበው ነጋዴ ጋር በስልክ እያወራሁነበር፡፡100 እንጀራ በ3 ብር ሂሳብ ስንት ይሆናል የሚለውን ለማስላት ያ እንከፍ ነጋዴ ግማሽ ሰዓት ፈጀበት፡፡በመሃል ሲያዳምጠንየነበረው ሰላይ ተናደደ መሰል ከየት ገባ ሳንለው በዝምታው መሃል ጥልቅ ብሎ ‹‹አንት ደነዝ ማባዛት ሳትችል ነውንዴ ብር የምትቆጥር›› ብሎ ልብሱ እንዳይቀርአድርጎ ሞለ ጨው፡፡››

ኢህአዴግን እንዳይመርጥ የወሰነበትን ምክንያት ብዙ ነው፡፡በዚህ ሰው ጭንቅላት ውስጥኢህአዴግ የሚለው ቃል ከታላላቅ ስድቦች ጋር ይመሳሰልበታል፡፡በአንድ ወቅት አንድ ጓደኛው ከስድቦች ሁሉ ትልቁ ‹ባለጌ› የሚለውነው ብሎት ነበር፡፡እንደ ጓደኛው አነጋገር ባለጌ የሚለው ቃል ውስጥ የማይወድቅ መጥፎ ድርጊት የለም፡፡ሌብነት ‹ባለጌነት› ነው፡፡ሰካራምነት‹ባለጌነት› ነው፡፡ነውረኝነት ‹ባለጌነት› ነው፡፡ሆዳምነት፣ጨካኝነት ፣አይረቤነት ባለጌነት ነው፡፡ታሪክ አዋራጅነት፣ትውልድ ሻጭነት፣ህልምአምካኝነት ‹ባለጌነት› ነው፡፡ከብዙ አመታት በኃላ ባለጌ የሚለውን ስድብ የሚበልጥ ስድብ እንደተፈጠረ ይሄ ሰው ያምናል፡፡ያም ስም‹ኢህአዴግ› የሚለው ቃል ነው፡፡

ኢህአዴግን ለመምረጥ የማይፈልገው ለዚሁ ነው፡፡ቢሆንም እናቱ ያሉትን ስጋት መርሳትአይቻልም፡፡ካቀረቀረበት ቀና ብሎ ዙሪያውን ቀኘ ከጠባቧ የድምጽ መስጃ ጣሪያ ላይ ካሜራ መኖር አለመኖሩን አረጋገጠ፡፡ካሜራ የለም፡፡ስለሆነምኢህአዴግን ባለመመረጥ ውሳኔው ጸንቶ ወደ ሌሎቹ ምልክቶች አቀረቀረ፡፡

የስኪርቢቶውን ክዳን እያኘከ በዝምታ ቆየ፡፡የቱን ፓርቲ እንደሚመርጥ ግራ ገባው፡፡የእናቱድምጽ ዳግም ተመለሰ፡፡

‹‹የኢትዮጵያ ህዝቦች መጽናኛ ፓርቲን ምረጥ፡፡በምርጫ ቅስቀሳ ጊዜ ስልጣን ከያዝንየመጀመሪው ስራችን የቀድሞ ባለ ስልጣናትን ልብሳቸውን አስውቆ አርባ መግረፍ ነው ሲሉ ሰምቻለሁ፡፡››

‹‹እነሱን አልመርጣቸውም…››
‹‹ለምን?››
‹‹ ሬድዋን ሁሴንን ማን ራቁቱን ያያል፡፡ለብሶም ይዘገንነኛል፡፡››
‹‹እሺ የኢትዮጵያ ህዝቦች ምኞት ህብረትን ምረጥ፡፡የሀገሪቱ ችግር የጓድ መንግስቱአለመኖር ስለሆነ እሳቸው እንዲመለሱ እናደርጋለን ሲሉ ሰምቻቸዋለሁ፡፡››
‹‹እነሱንም አልመርጣቸውም፡፡››

‹‹ምን አጠፉ?››
‹‹መንግስቱ ሃ/ማሪያም እኮ አሁንም ስልጣን ላይ አለ፡፡ትንሽ ቁመትና ሞኝነት ጨመረእንጂ ››
‹‹ምን ደህና ደህና ሰዎችን ለቃቅሞ እስር ቤት ከትቶብን አኮ ነው ለምርጫ የተቸገርነው፡፡የዘንድሮውምርጫ እኮ መካሄድ የነበረበት ቃሊቲና ዝዋይ ነበር፡፡ባዶ የዕጣ ጥቅሎችን በትሪ ላይ እያንጓለሉ ‹‹በሉ አንዱን ምረጡ›› አይነትጨዋታ ሆነብን እኮ፡፡ለምን የሰገሌ ህዝቦች ነጻ አውጪ ፓርቲን አትመርጥም…››
‹‹ደግሞ እሱ የትኛው ፓርቲ ነው?››

‹‹ይሄ ካሸነፍኩ የሰገሌ ህዝቦችን ከመላ ሃገሪቱ እገነጥላለሁ ያለው ነዋ፡፡››
‹‹እሱን ታዲያ በቦክስ መገንጠል እንጂ የምናባቱ ድምጽ መስጠት ነው፡፡እስቲ ወንድየሆነ ይገነጠላታል፡፡ከሚስቱ የተኮራረፈ ሁሉ መኝታ ቤቴን ይዤ እገነጠላለሁ ሊል ምንም አልቀረውም እኮ፡፡ ሌሎች ነፍስ ያላቸው ፓርቲዎችየሉም?››
የእናቱ መልስ አይጠፋውም -አሉ፡፡ግን ቢያሸንፉም አያሸንፉም፡፡ እንቅልፋሙን ፓርላማእንቅልፍ የሚነሱ ጥሩ ምሁራን ነበሩ፡፡የተናገሩት አድማጭን ሚያሳድግ የሚሰነዝሩት ተመልካችን የሚያነቃ ጎበዝ ሊቆች ነበሩ፡፡ህዝብበጅምላ እንዳልመከነ የሚያሳዩ ናሙናዎች አሉ፡፡ሁለት አይነት ሰዎች አሉ፡፡አንደኞቹ ከሚበልጣቸው ሊቆች ጋር እየዋሉ እራሳቸውን ለመስተካከል የሚጥሩ፡፡ሁለተኞቹ የሚበልጣቸውን ሊቅአሰድደው ‹እኔ ነኝ የቀረኋችሁ ሊቅ !›የሚሉ፡፡መንግስት ከሁለተኛው ይመደባል፡፡ባለው ሃቅም ልሂቃኑ ከአጠገቡ እንዳይቀመጡ ይተጋል፡፡የምርጫወቅት ይሄ የመንግስት ኢያጎአዊ ጠባይ የሚገለጥበት ነው፡፡ሚሊየን ሰው ልሂቃኑን ይምረጥ ቢሊየን አውጥቶ ድምጻቸውን ይዘርፋል፡፡
‹‹እንደዚህ ከሆነ ለምን እመርጣለሁ!›› አለ በድንገት፡፡
‹‹ድምጼ የማይቆጠር -ሃሳቤ የማይከበር ከሆነ ለምን እመርጣለሁ?››
‹‹ለአለም በሚያሳዩት የሳውቅዮሽ አውጫጭኝ መሃል ለምን እዳክራለሁ?››
‹‹በባሩድና በሚታጠን በድንጋይ በሚከበብ ወር መሃል ስለምን እቆማለሁ?››
የድምጽ መስጫ ወረቀቱን አጣጥፎ በኪሱ ከተተ፡፡እስኪርቢቶውን በደረት ኪሱ ውስጥአስገባ፡፡ከተከለለው ጠባብ የድንኳን ክፍል ሊወጣ ተሰናዳ፡፡
የእናቱ ድምጽ መጣበት
‹‹ሊቢያ ላይ የተሰውት ወጣቶች ገዳዮቻቸውን አሳፍረው ሞሞታቸውን ሰማሁ ልበል?››
‹‹አዎ እማዬ አለም እያወራበት ነው፡፡በሞት አፋፍ ላይ ሆነው ሁሉ ጠላቶቻቸው ይፈልጉትየነበረውን ፍርሃት እና ለቅሶ እና መሰበር ሳያሳዩ ማለፋቸው ብዙ ሰውን አስገርሟል፡፡››

‹‹ አየህ ቶሎ አልተገለጠልንም እንጂ – ጀግንነት ጠላትህ ከሚፈልገው ተቃራኒ ቆሞበማሳየትም ይገለጣል፡፡አቀርቅር በሚባልበት ሰዓት ቀና ማለት ጀግንነት ነው፡፡ዝምበል በተባልክበት ሰዓት መናገር ጀግንነት ነው፡፡ቁምበተባልክበት ሰዓት መራመድ ጀግንነት ነው፡፡እርምህን አውጣ በተባልክበት ሰዓት ተስፋህን ማሳደግ ጀግንነት ነው፡፡ትልቁ ሞት ሳይሞክሩመሞት ነው፡፡››

የድምጽ መስጫ ወረቀቱን ከኪሱ አወጣ፡፡እስኪርቢቶውን ከደረት ኪሱ መዘዘ፡፡በምልክቶቹላይ አይኑን አበረረ፡፡ከሆነ ምልክት ፊት ለፊት ባለው ሳጥን ውስጥ የኤክስ ምልክት አደረገ፡፡

ምልክቱን ከገዥው ፓርቲ ምልክት ፊት ለፊት አለማድረጉን ያውቃል፡፡
ባለጉም ሃሳቦች ከመሰረቷቸው ተቃዋሚ ፓርቲዎች ፊት ለፊት አለማድረጉን ያውቃል፡፡
ሲረገጡ መሬት ይዘው የሚነሱ ሊሂቃን እና ተስፋዎች የተሰባጠረው ፓርቲ ፊትለፊትምልክት ማድረጉን ብቻ አረጋጧል፡፡የድምጽ ወረቀቱን አጣጥፎ ፈንጠር ብሎ በሚገኘው ሳጥን ውስጥ ጨመረው፡፡በር ላይ ከምርጫ አስተባባሪዎችአንዱ ‹በሰላም ነው ብዙ ጊዜ ፈጀብህ እኮ ….›› ሲል ስሞታ አቀረበበት፡፡
‹‹አንዳንዴ ለመጀገን ጊዜ ይፈጃል›› ብሎት ከምርጫ ጣቢያው ራቀ፡፡

The post መጀገን – በምርጫ ቀን appeared first on Zehabesha Amharic.

ሙስሊሙ እና ምርጫ

0
0

Muslim in ethiopia
ረቡእ ግንቦት 12/2007

ድምጻችን ይሰማ!
አላሁ አክበር!

ምርጫ የአንድ አገር ህልውና በህዝብ ውሳኔ እልባት የሚያገኝበት ሂደት ነው፡፡ በዚህም ማህበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ የውጭ ግንኙነት ወዘተ አማራጮች ለህዝብ ቀርበው ሁሉም እንደየፍላጎቱ ድምፁን በመስጠትም ይሁን ድምፁን በመንፈግ ይሁንታውን ገልፆ የፈለገውን የሚመርጥበት፣ ያልፈለገውን የሚያስወግድበት ስርዓት ነው፡፡ አሁን በአገራችን በቅርቡ የሚደረገው የምርጫ ስርዓትም ቢሆን በዚሁ ፅንሰ ሀሳብ መሰረት የሚደረግ መሆኑ ይታወቃል፡፡ ‹‹ህጉና ስርዓቱ በአግባቡ ስራ ላይ ይውላል›› የሚለው እንደተጠበቀው የመሆኑ ጉዳይ እንዳለ ሆኖ ማለት ነው፡፡

እኛ ሙስሊሞች ላለፉት 3 ዓመታት የመብት ጥያቄ አንስተን፣ ወኪሎቻችንን መርጠን በአግባቡ እና ስርዓቱን በተከተለ ህጋዊ መልኩ ስናቀርብ አሁን ስልጣን ያለው መንግስት ‹‹ለጥያቄያችን አግባብ የሆነ መልስ ይሰጠናል›› ከሚል እሳቤና ተስፋ በመነሳት መሆኑ እሙን ነው፡፡ ነገር ግን ያነሳናቸው መሰረታዊ ጥያቄዎች በአግባቡ መልስ ሳያገኙ፣ ከመረጥናቸው ወኪሎቻችን ከፊሎቹ እና ሌሎች በርካታ ወንድምና እህቶቻችን፣ እንዲሁም ኢማሞቻችን እና ዳዒዎቻችን ለእስር፣ ለእንግልት እና ለስደት ተዳርገውብናል፡፡ ምግባረ ሰናይ ድርጅቶች (NGO) ተዘግተዋል፡፡ ሚዲያዎች ከህትመት ውጪ ሆነውብናል፡፡ አሁንም ቢሆን በህዝበ ሙስሊሙ ላይ ጫና እየተደረገ ያለ መሆኑም እንደረፋድ ጸሐይ ግልጽ ነው፡፡ የፍትህ ስርዓቱም የተንዛዛና ተስፋ አስቆራጭ፣ እንዲሁም ተዓማኒነት የጎደለው መሆኑ በግልጽ ታይቷል፡፡ ይህ ምርጫ ተደረገም አልተደረገም ጥያቄዎቻችንን እና ብሶታችንን ሁሉ ምላሽ እስኪያገኙልን እና ወኪሎቻችን፣ እንዲሁም ሌሎች እስረኞቻችን እስኪፈቱልን ድረስ በፅናት ትግላችንን መቀጠል እንዳለብን ሁላችንም መገንዘብ ይኖርብናል፡፡

ምርጫውን አስመልክቶ የሚወሰነው ውሳኔ ፖለቲካዊ ውሳኔ እንደመሆኑ መጠን በአንዳንድ ወገኖች ‹‹የህዝበ ሙስሊሙ ጥያቄ ወደ ፖለቲካ ጥያቄነት ተቀይሯል›› የሚል የተሳሳተ አመለካከት እንዳለ ተረድተናል፡፡ አሁንም ሆነ ወደፊት ሊታወቅ የሚገባው ህዝበ ሙስሊሙ ያነሳቸው ጥያቄዎች ሃይማኖታዊ እና ሃይማኖታዊ መሆናቸው ብቻ ነው፡፡ ወደፊትም ይህን ይዘቱን ሳንለቅ ለመብታችን መከበር እንታገላለን! ከላይ ለመግለፅ እንደሞከርነው ፖለቲካ የአንድን አገር የኢኮኖሚ፣ ማህበራዊ፣ የውጭ ግንኙነት ወዘተ ፖሊሲዎች የሚነደፉበት እና የአገሪቱ መፃዒ ዕድል የሚወሰንበት ሰፊ ስርዓት ከመሆኑ አኳያ ህዝበ ሙስሊሙ ካነሳቸው ሃይማኖታዊ ጥያቄዎች ጋር ግንኙነት የለውም፡፡

ማንኛውም ሙስሊም ከላይ ያሉት የአንድ አገር ህልውና የሚረጋገጥባቸው ፅንሰ ሀሳቦች ለተካተቱበት የፖለቲካ ምርጫ ‹‹ይበጀኛል›› የሚለውን፣ ለአገራችን ህዝቦች፣ ብሄር ብሄረሰቦች፣ ለውጭ ግንኙነቶች፣ በአጠቃላይ ለህልውናው እና ለሙሉ መብቱ ይጠቅማል የሚለውን አማራጭ በማገናዘብ እና በመፈተሽ ድምፁን ላሻው ፓርቲ የመስጠት ሙሉ መብቱን መጠቀም እንዳለበት እናምናለን፡፡ ይህን መናገር መብቱን ማስታወስ እንጂ ‹‹ፖለቲካዊ አቋም መያዝ››፣ አልያም ‹‹የትግሉን ዓላማ ፖለቲካዊ ማድረግ›› ማለት እንዳልሆነ ግን ግንዛቤ ሊወሰድ ይገባል፡፡

በተነጻጻሪ መልኩ ከዚህ ምርጫ በፊትም ሆነ በኋላ ባለፉት 3 ዓመታት ኢትዮጵያዊው ሙስሊም ባካሄደው ትግል የታየው አስደማሚ ሰላማዊ የመብት ጥያቄ እንቅስቃሴያችን አሁንም መቀጠል ይኖርበታል፡፡ እምነታችን ረብሻን፣ ስርዓት አልበኝነትን እና የሌሎችን መብት መንካትን አይፈቅድልንምና በዚሁ መሰረት መብቶቻችን ሁሉ ተከብረው፣ የጀመርነው ሰላማዊ የመብት ጥያቄ ዳር እስኪደርስ እና በድል እስከምናጠናቅቅ ድረስ ትግላችንን በፅናት እንቀጥላለን!

ትግላችን እስከድል ደጃፎች በአላህ ፈቃድ ይቀጥላል!

The post ሙስሊሙ እና ምርጫ appeared first on Zehabesha Amharic.

የአሜሪካ እርዳታ አምባገነኖችን ማጠናከሩ ይቁም –ግልፅ ደብዳቤ ለአሜሪካ መንግሥት ሃላፊዎችና ለአሜሪካ ሕዝብ

0
0

 

ከአክሎግ ቢራራ (ዶ/ር)

ከአክሎግ ቢራራ (ዶ/ር

ከአክሎግ ቢራራ (ዶ/ር

የኢትዮጵያና የአሜሪካ ግንኙነት ከመቶ ዓመታት በላይ ነው። ይኼ ግንኙነት በሁለቱ ሃገሮች መካከል ሊኖር የሚገባውን የእኩልነትና የጋራ ጥቅም መሰረት ያደረገ እንደ ነበረ ታሪክ ያስታውሳል። መንግሥታት ቢለዋወጡም በሁለቱ ሃገሮች መካከል የተመሰረተው የቆየ ግንኙነት አይፈርስም የሚል እምነት አለኝ። የኢትዮጵያ ስደተኞች አሜሪካን የመጀመሪያ መድረሻ አድርገን አሜሪካዊ የሆንንበትና ወደፊትም የምንሆንበት ዋና ምክንያት የአሜሪካ አስኳል እሴቶች–ነጻነት፤ የግለሰብ ክብር፤ ፍትህ-ርትእ፤ የሰብአዊ መብቶች መከበር፤ በሕግ ፊት ማንኛውም ግለሰብ እኩል መሆን፤ የሕግ የበላይነትና ዲሞክራሳዊ አገዛዝ ስለሳቡንና የመስራት እድል በጎሳ ሳይሆን በሞያ የሚወሰን መሆኑን ስላወቅን ነው። ዛሬ ብዙ መቶ ሽህ የኢትዮጵያ ትውልድ በአሜሪካ ይኖራል፤ ድምጽና መብት አለው። በኢትዮጵያ የማናገኘውን በተሰደድንበት አሜሪካ እናገኛለን። ይኼን እድል ተጠቅመን ለተወልድንባት ሃገር ጠበቃ እንሁን።

በሁለቱ ሃገሮች የተመሰረተው የቆየ ግንኙነት በወታደራዊው፤ ሶሻሊስት አምባገነን መንግሥት ዘመን ተለውጦ አሜሪካኖች አቋማቸውን ለውጠው ተተኪ መንግሥት ይጠባበቁ እንደ ነበር ብዙ ማስራጃዎች አሉ። ደርግን የተካው የጎሳ ልሂቃን ቅንጅት ህወሓት በበላይነት የሚያሽከረክረው የኢህአዴግ መንግሥት ከምእራብ ሃገሮች፤ በተለይ ከአሜሪካ ጋር ያለው የጥቅም ትሥስር እጅግ በጣም የጠነከረ ነው። የኢትዮጵያ እድገት ፈጣን የሆነው በውጭ እርዳታ፤ ስደተኛው በሚልከው ገንዘብ፤ በሃገር ውስጥ ብድርና በቅርቡ በውጭ ኢንቬስተሮች ድጋፍ ነው። ኢኮኖሚው በራሱ ለመንቀሳቀስ አልቻለም፤ ፍትኅ ከሌለ አይችልም። በአሜሪካኖች ስሌት፤ በፈራረሰው፤ እርጋታና ሰላም በሌለበት የአፍሪካ ቀንድና አካባቢ (በሰሜን ኤርትራ፤ በምስራቅ፤ ሶማሊያ፤ በምእራብ ደቡብና ሰሜን ሱዳን፤ በባህር ማዶ በየመን፤ በሶሪያ፤ በኢራክ፤ በሰሜን አፍሪካ በሊብያና በግብፅ) ያለውን የርስ በርስ ግጭት፤ የሃገሮች መፈራረስና የሃብት ውድመት ሲመለከቱ ኢትዮጵያ “የእርጋታና የልማት” ደሴት ናት ወይንም ትሆናለች ብለው ማመናቸው አያስገርምም። ግዙፉ እርዳታ ከዚህ ስሌት ጋር ቀጥተኛ ግንኙነት አለው። ጸረ-ሽብርተኛነት ሰብሳቢ መርህ ሁኗል። አሜሪካኖች ያላስተዋሉት፤ ቢያስተውሉትም የሚመጣውን ችግር ከራሳቸው ጊዚያዊ ጥቅም ባሻገር ያልተገነዘቡት፤ አምባገነኖች ፀረ-ሽብርተኛነትን ምክንያት በማድረግ ራሳቸው ሽብር ፈጣሪዎችና ሽብርተኞች መሆናቸውን ነው። የሰብአዊ መብቶችና የነጻነት መገፈፍ ሁለተኛ ወይንም ሶስተኛ ደረጃ የያዘው ለዚህ ነው። የሕዝብ መብቶች በተከታታይ ሲጎዱ አፍራሽ ኃይሎች፤ ሽብርተኞችን ጨምሮ መግቢያ ቀዳዳ ያገኛሉ፤ ስደተኝነት እየከፋ ይሄዳል።

የአሜሪካ መንግሥት መሪ ፕሬዝደንት ባራክ ኦባማ ልክ የዛሬ ሁለት ዓመት በደቡብ አፍሪካ እንዲህ ብለው ነበር። “በአፍሪካ ሃገሮች በሙሉ የማንኛውም ግለሰብ ክብር ቢከበር አሜሪካኖችም ነጻ ይሆናሉ። እኔ የማምነው እያንዳንዳችን ነጻ ለመሆን ከተፈለገ የሁሉም ሰብአዊ ቤተሰቦችና ግለሰቦች ከድህነት ወይንም ከበሽታ ወይንም ከጭቆና ነጻ መሆን አለባቸው።” ይኼ እሴት የአሜሪካኖች እሴት ነው፤ የመላው በነጻነት ለመኖር የሚፈልግ ሕዝብ እሴትና ተስፋ ነው። የኢትዮጵያ ሕዝብ ለክብሩ፤ ለፍትህ፤ ለነጻነት፤ ለሕግ የበላይነትና ለዲሞክራሲ ሲታገል ከዓመሳ አመታት በላይ ሁኗል። ኢትዮጵያ ባለፉት ሃያ አምስት ዓመታት በአንድ አምባ ገነን ፓርቲ ስትገዛ ቆይታ አሁንም በአራት ቀናት በሚካሄድ “የይስሙላ ምርጫ” የተጠበቀ ውጤት ለሚከተሉት አምስት አመታት ትገዛለች። የኢትዮጵያ የመንግሥት ስርዓት ልክ የፈረሰውን የሶቬት ሕብረት አገዛዝ የሚመስል ጋርዲያን የተባለው ጋዜጣ “ኦርዌሊያን” የሚለው፤ ወይንም በእኔ አመለካከት ፍጹም የሆነ በስለላ መረብ የተቆራኘ፤ በአንድ አናሳ ብሄር የበላይነት የመከላከያ፤ የስለላና የኢኮኖሚ የበላይነት የሚተዳደር አገዛዝ ነው።

ይኼ አገዛዝ ያለ ዓለም ትሥስር የገንዘብ የስለላ፤ የመከላከያ፤ የዲፕሎማሲና ሌላ ድጋፍ ህይወት አይኖረውም። የማይካደው ገዢው ፓርቲ ባለፉት ሃያ አራት አመታት ለልማት ድጎማ ብቻ አርባ ቢሊየን ዶላር ተሰጥቷታል። ኢህአዴግ ከሙስናው፤ ከሃገር በገፍ እየተሰረቀ ከሚሸሽውና ከሌላው ውድመት የተረፈውን ተጠቅሞ መሰረተ ልማት አካሂዷል። ከእድገቱ ባሻገር መታየት ያለበት ሃቅ፤ ባለፉት አራት ዓመታት ብቻ የምግብ እርዳታ ጥገኛ ከሆነችው፤ ወጣቱ ትውልድ በገፍ ከሚሰደድባት ኢትዮጵያ ተሰርቆ የሸሸው ሃብት ግምት አስር ቢሊየን ዶላር ነው። ይኼ ስንት ፋብሪካ ይከፍት ነበር፤ ለስንት ወጣቶች የስራ እድል ያቀርብ ነበር? የተሰረቀው ተሰርቆና ከሃገር ሸሽቶ፤ የተረፈው መንገድ ስርቷል፤ ሃዲድና ግድቦች እየሰራ ነው። ይኼ ግዙፍ እርዳታና መንግሥት ከባንኮች ተበድሮ ሰማይ ጠቀስ ፎቆች፤ ቪላዎች፤ መንገድና ሌላ ቢሰራ ምኑ ያስደንቃል? የማይካደው ኢትዮጵያ ከመቸውም ጊዜ በበለጠ ደረጃ ጥገኛ መሆኗ ነው። ኢትዮጵያ ዛሬ በያመቱ የአራት ቢሊየን ዶላር እርዳታ ተቀባይ ሁናለች፤ ከአፍሪካ ከፍተኛው ከሆነ ቆይቷል። በመንግሥት ደረጃ ሲታይ ከሁሉም ሃገሮች ከፍተኛውን እርዳታ የምትለግሰው አሜሪካ ናት። ፈጣን እድገት አለ በሚባልባት አዲስ አበባ ከፎቆቹ ባሻገር ለማየት ለፈለገ ታዛቢ ቢያንስ አንድ መቶ ሽህ ህፃናት በመንገድ ያድራሉ፤ ብዙ መቶ ሽህ ነዋሪዎች ምግብ ከቆሻሻ ማጠራቀሚያ እየለቀሙ ይበላሉ። ከስምንቶ መቶ ሽህ እስከ አንድ ሚሊየን የኢትዮጵያ ስደተኞች በየመን ብቻ ይገኛሉ። በሊቢያ የታጎሩትን ቁጥር አናውቅም። ለጋሶች ይኼን ሁሉ ግፍ አያውቁም ለማለት አልችልም። በተጨማሪ፤ መጭው ምርጫ ለይስሙላ መሆኑን የአሜሪካ መንግሥት ያውቃል። ጠቅላይ ሚንስትር ኃይለማሪያም ደሳለኝ የያዘው ስራ ይረጋገጥለታል፤ አሜሪካኖች ይኼን እንደሚደግፉ አልጠራጠርም። ሕዝብ የፈለገውና እውነተኛ ውድድር ያለበት ምርጫ ቢሆን ኑሮ፤ የአሜሪካ ኢምባሲና የተባበሩት መንግሥታት ድርጅቶች በምርጫው ቀንና ተከታታይ ቀኖች “ብጥብጥ” ይነሳል በሚል ስሌት የተጠንቀቁ መልእክቶች አያወጡም ነበር።

ከላይ የቀረበውን መሰረት በማድረግ አሜሪካኖችን የጠየቅኋቸውና ያሳስብኳቸው የእርዳታውን ጥቅምና ጉዳት ከራሳቸው መብትና ጥቅም አንፃር እንዲያዩት ነው። “እስኪ አስቡት፤ በአሜሪካ በተከታታይ አንድ ፓርቲ በየ አራት አመቱ በሚደረገው ምርጫ ቢያሸንፍ ምን ትላላችሁ? የፖለቲካ ተወዳዳሪዎች መብታቸውን ለማስከበር ሰላማዊ ሰልፍ ሲወጡ ፖሊስ ቢደበድባቸው፤ ቢያስራቸው፤ ቢያሳድዳቸው ምን ትላላችሁ? ምርጫው ሰፊ ውድድር ተካሂዶ የፖሊሲ አማራጮች ውይይት ባይደረግባቸው ምን ትላላችሁ? አስቡት፤ ኢትዮጵያ ከአርባ ቢሊየን ዶላር እርዳታ በኋላ ከዓለም ሃገሮች መካከል አሁንም ፍፁም ድሃና በዓመት የነፍስ ወከፍ ገቢዋ ከአፍሪካ ሃገሮች አንድ ሶስተኛ የሆነ፤ ከዓለም ሃገሮች መካከል በሙሰኛነት የተበከለች፤ ከዓለም ሃገሮች መካከል ከፍተኛውን የምግብ ጥገኝነት ቦታ የያዘች፤ በአፍሪካ ጋዤጠኞችን ከሚያስሩ ሃገሮች መካከል ሁለተኛውን ደረጃ የያዘች፤ በዓለም ደረጃ አራተኛውን ደረጃ የያዘች መሆኗን ብታውቁ ምን ትላላችሁ? ይህች የምግብ ጥገኛ የሆነችው ኢትዮጵያ አብዛኛውን የምግብ እርዳታ የምታገኘው ከአሜሪካ መንግሥት ነው። ከድሃይቱ ኢትዮጵያ በአራት ዓመታት ብቻ አስር ቢሊየን ዶላር ተሰርቆ ሲሸሽ ለሃገር ጥቅም ቢውል ኑሮ ስንት ፋብሪካዎች ለማቋቋም እንደሚያስችልና ለስንት ኢትዮጵያዊያን የስራ እድል እንደሚፈጥር አስቡት?

እኔ ይኼን ሃተታ ለአሜሪካ ሕዝብና መንግሥት በታወቁ ጋዜጦች አማካይነት ለማቅረብ የተገደድኩት በሙስናውና በገንዘቡ መሰረቅ ምክንያት አይደለም። ያሳሰበኝ፤ የኢትዮጵያዊያን ሰብ አዊ መብቶች በተከታታይ መገፈፋቸው፤ የማህበረሰብ ድርጅቶች፤ ነጻ ጋዜጦችና ጋዜጠኞች፤ ተወዳዳሪ ሊሆኑ የሚችሉና የተሻለ አማራጭ ለሕዝብና ለሃገር ለማቅረብ የሚችሉ የፖለቲካ ፓርቲዎች መደምሰሳቸው፤ መናገር፤ መሰብሰብ፤ መንግሥትን መተቸት ወንጀል መሆኑ ነው። እነዚህን እሴቶች እንደምታከብሩና እንደምትታገሉላቸው አምናለሁ። ታዲያ፤ የአሜሪካ መንግሥት የሚሰጠው እርዳታ እነዚህን እሴቶች ካላጠናከረ ዘላቂ ጥቅሙ ምንድን ነው? የመናገር፤ የመሰብሰብ፤ የመከራከር፤ የመተቸት፤ የመወዳደር ወዘተ መብቶች ፍጹምና አደገኛ በሆነ ደረጃ ታፍነዋል። ሂውማን ራይትስ ወች እንዲህ ሲል አስጠንቅቆ ነበር። “የኢትዮጵያ መንግሥት በአሰቃቂ ደረጃ ከመንግሥት ቁጥጥር ነጻ የሆነውን መገናኛ ብዙሃን አውድሞታል፤ ቢያንስ ሃያ ሁለት ጋዜጠኞች፤ አሳታሚዎችና ብሎገሮችን በወንጀለኛነት ከሶ አስሯል፤ ከሰላሳ በላይ ጋዜጠኞች በፍርሃት ከሃገር እንዲሰደዱ አድርጓል።” ገዢው ፓርቲ ይኼን ሲያደርግ የሚጠቀምባቸው በ2009 ያፀደቃቸው የጸረ-ሽብርተኛና የመንግሥት ያልሆኑ የበጎ አድራጎትና የማህበረሰብ ድርጅቶችን የሚመለከቱ ሕጎችን ነው። ለነጻነት፤ ለፍትህ፤ ለዲሞክራሲና ለሕግ የበላይነት የተሟገተና የቆመ ግለሰብ ሁሉ ሰለባ የመሆን እድሉ ከፍተኛ ነው። በስራ እድል በኩል ሲታይ፤ ለገዢው ፓርቲ ወይንም ለጎሳ ጥቅም ታማኝነት ያላሳየ ሁሉ እድል አይኖረውም። አስተዳደሩ በባለሞያዎች ሳይሆን በታማኝነት ይመራል። ይኼን ሁኔታ ስታዩ፤ አፈናው፤ አድልወው፤ ጭካኔው፤ መገለሉ ወዘተ ለሰላም፤ አብሮ ለመኖር፤ ለእርጋታ አደገኛ መሆኑን ትገምታላችሁ። የአገዛዙ አፋኝነትና አግላይነት ለሽብርተኛነት አመች ሁኔታ ፈጥሯል። የአሜሪካ መንግሥት እንደዚህ ያለ አፋኝና አግላይ መንግሥት ሲደግፍ የአሜሪካን የረዢም ጊዜ ጥቅም ይጎዳል ወይንስ አይጎዳም? ብላችሁ የመጠየቅ ሃላፊነት አለባችሁ።

ይኼን አደጋ በተደጋጋሚ የምናቀርበው ኢትዮጵያዊያን ብቻ አይደለንም። በዚህ ዓመት ፍሪደም ሃውስ ስለ ዓለም ሃገሮች ነጻ መሆን አለመሆን ባወጣው ዘገባ ኢትዮጵያ ከአርባ ዘጠኝ ነጻ ካልሆኑ የአፍሪካ ሃገሮች መካከል አርባ ሶስተኛውን ደረጃ ይዛለች፤ ከኢትዮጵያ የባሱ ስድስት ሃገሮች ብቻ አሉ ማለት ነው። በተመሳሳይ፤ ዘ ኮሚቲ ቱ ፕሮቴክት ጆርናሊስትስ የተባለው ተቋም “ጋዜጠኞችን በከፍተኛ ደረጃ ከሚያስሩ ሁለት የአፍሪካ ሃገሮች መካከል አንዷ መሆኗን፤ በዓለም ደረጃ ሲታይ አራተኛ መሆኗን አመልክቷል። እንደዚህ ጨለማ በሆነ ሁኔታ ነጻና ፍትሃዊ ምርጫ ሊካሄድ አይችልም። ምርጫውን በሚመለከት በዚህ ወር ሂውማን ራይትስ ወች “ምርጫ–የኢትዮጵያን ፈለግ የተከተለ” በሚል እንዲህ ከሚል ድምዳሜ ላይ ደርሷል። “ካለፈው ምርጫ ወዲህ፤ ገዢው ፓርቲ በባሰ ደረጃ ቁጥጥሩን አጠናክሯል፤ የመናገር፤ የመሰብሰብ፤ የመደራጀት መብቶችን ከልክሏል… ኢትዮጵያዊያን ወደ ምርጫ ሲሄዱ ተቃዋሚዎች በገጠማቸው አፈና የተነሳ ያላቸው እድል በጣም የጠበበና ጨለማ የሆነ ነው።” የኢትዮጵያን ሕዝብ፤ በተለይ ተቃዋሚውን በንቀት መነፅር ያየችው የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ምክትል የፖለቲካ ሃላፊ ዌንዲ ሸርማን “ኢትዮጵያ ዲሞክራሲ ናት፤ ምርጫውን በሚመለከት ነጻ፤ ፍትሃዊ፤ ተቀባይነት ያለው፤ ክፍትና ሁሉን አቀፍ የሆነ ምርጫ እንደሚካሄድ እናምናለን” ያለችው ውሸት ብዙ የምእራብ ታዛቢዎችን ቁጣና ትዝብት አምጥቷል። ዋሽንግተን ፖስት የተባለው የታወቀ ጋዜጣ እሷንና የኢትዮጵያን መንግሥት በሚመለከት “የማስመሰል ምርጫ በኢትዮጵያ” በሚል አርእስት እንዲህ ብሏል። “የአሜሪካ መንግሥት የኢትዮጵያን መንግሥት ማውገዝ እንጅ ማሞገስ የለበትም።” ስለሆነም፤ የአሜሪካን መንግሥትና ሕዝብ አደራ የምለው ሽብርተኛነትን ለመከላከል በሚል ምክንያት ሽብርተኛነትን የሚፈጥርና የሚያጠናክር መንግሥት መደገፉን ያቁም ነው።

ምን አማራጭ አለ?

ጠቃሚውን ተቃውሞ ለመቀበል ፈቃደኛ የሆነን ግለሰብ ወይንም መንግሥት ለማሳመን አስቸጋሪ ነው። በእኔ ግምት ለኢትዮጵያ ዘላቂነት፤ ለመላው ሕዝቡ የኑሮ መሻሻል፤ ለአሜሪካ ዘላቂ ጥቅም አጋባብ ያለው አማራጭ ያለምንም ማወላወል ለሰብአዊ መብቶች፤ ለነጻነት፤ ለፍትህና ለሕግ የበላይነት መከበርና ለዲሞክራሲ ግንባታ ያለተቆጠበ ድጋፍ መስጠት ነው። ቢያንስ የአሜርካ መንግሥት ለራሱ ዘላቂ ጥቅም ሲል የሚለግሰውን እርዳታ በሙሉ ከሰብ አዊ መብቶች መከበርና ከዲሞክራሲ ግንባታ ጋር ማጣመር አለበት። ነጻ፤ ፍትሃዊ፤ ተቀባይነት ያለው፤ ክፍትና ውድድር ያለበት ምርጫ ለማካሄድ ቅድመ ሁኔታዎች መከበር ነበረባቸው። አለመከበራቸው ውጤቱን አስቀድሞ ወስኖታል። ገዢው ፓርቲ ያሸንፋል።

የአሜሪካን ሕዝብ፤ የምክር ቤት አባላትንና የመንግሥት ሃላፊዎችን በቀጥታ የምጠይቀው ከሕዝብ ተሰብስቦ ለኢትዮጵያ አምባገነን መንግሥት የሚሰጠው እርዳታ ከዲሞክራዊው አገዛዝ ጋር ምን ግንኙነት አለው፤ ከሌለው ለምን ለሰብአዊ መብቶች፤ ለነጻነት፤ ለፍትህ፤ ለእውነተኛ እኩልነትና ለዲሞክራሲ አትቆሙም? የሚል ነው።”

በእኛ በኩል አብሮና ተባብሮ ከመስራት ሌላ አማራጭ የለንም። የአሜሪካ ዜግነት ያለን ኢትዮጵያዊያን በያለንበት ለአሜሪካ ምክር ቤት ተወካዮች ሳንሰለች ድምፃችን ብናሰማ ከፍተኛ አስተዋፆ እንደምናደርግ አምናለሁ፤ እስቲ ያልሞከርነውን እንሞክር እላለሁ።

 

 

 

The post የአሜሪካ እርዳታ አምባገነኖችን ማጠናከሩ ይቁም – ግልፅ ደብዳቤ ለአሜሪካ መንግሥት ሃላፊዎችና ለአሜሪካ ሕዝብ appeared first on Zehabesha Amharic.

ኢዴፓ በዕጩዎቹ ላይ እንግልት እየደረሰባቸው ቢሆንም በምርጫው እንደሚገፋ አስታወቀ

0
0

EDPAየፊታችን እሑድ በሚደረገው ጠቅላላ ምርጫ ተሳታፊ የሆነው የኢትዮጵያውያን ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (ኢዴፓ) በዘንድሮ የምርጫ ተሳትፎው ላይ በርካታ ችግሮች እየገጠሙት ቢሆንም፣ በምርጫው እስከ መጨረሻው ድረስ ተሳትፎው እንደሚቀጥል አስታወቀ፡፡

‹‹ለመርሆዋችን ተገዥ በመሆን የምርጫ ተሳትፎአችን እስከ መጨረሻው ይቀጥላል፤›› በሚል ርዕስ ለሪፖርተር በላከው መግለጫ፣ በምርጫ ተሳትፎው ላይ እየደረሱ ነው ያላቸውን ችግሮች ኢዴፓ ገልጿል፡፡

ፓርቲው ያገኛቸውን ነፃ የአየር ሰዓቶች በመጠቀም አማራጮቹን ለሕዝብ እንዳያደርስ በሚዲያ ተቋማት የደረሰበትን ሳንሱር፣ በየክልሉ በሚወዳደሩ ዕጩዎቹ ላይ የማዋከብ፣ የማስፈራራት፣ ስም የማጥፋትና የመደብደብ ዕርምጃዎች ተጠናክረው መቀጠላቸው፣ ዕጩዎቹና ደጋፊዎቹ ቅስቀሳ እንዳያደርጉ መከልከላቸው፣ የፖስተር መቀደድ እንደ ገጠመው፣ ባነሮችን ከቦታቸው ላይ መሰወርና ዕጩዎቹን ከሥራ ማባረር፣ ደመወዝ መከልከል፣ ከአገልግሎት ማግለልና የመሳሰሉት እየደረሱበት ካሉ ችግሮች መካከል ተጠቃሽ እንደሆኑ አስታውቋል፡፡

ኢዴፓ በዚህ መጠኑ ያለፈ ተፅዕኖ ምክንያት በክልል የሚገኙ ጥቂት ዕጩዎቹ ራሳቸውን ከምርጫ እንቅስቃሴ ለማግለል የሚያስገድዳቸው ሁኔታ እንደተፈጠረ በመግለጫው የጠቆመ ቢሆንም፣ የፓርቲው የጥናትና ምርምር ጉዳዮች ኃላፊ አቶ ዋሲሁን ተስፋዬ ግን ችግሩ በድርድር ተፈቶ አሁን ዕጩዎቹ ሥራዎቻቸውን በአግባቡ እያናወኑ መሆናቸውን አስታውቀዋል፡፡

አቶ ዋሲሁን፣ ‹‹ቁጫና ወላይታ ላይ አባሎቻችን ከሌሎች ፓርቲ አባላት ጋር በመሆን ከምርጫው ራሳቸውን እንደሚያገሉ ገልጸው የነበረ ቢሆንም፣ አሁን ግን ችግሩ በመፈታቱ ሥራቸውን ቀጥለዋል፡፡ የምርጫ ቅስቀሳውንም ሲያከናውኑ ነበር፤›› በማለትም አክለዋል፡፡

‹‹ፓርቲያችን እነዚህ ከመጠን ያለፉ ጫናዎች ቢኖሩም፣ አባሎቻችንና መዋቅሮቻችን ችግሩን ተቋቁመው በምርጫው ውስጥ የሚያደርጉትን ተሳትፎ እስከ መጨረሻው እንዲዘልቁበት ጥረት እየተደረገ ይገኛል፤›› በማለት በአስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ሆኖም በምርጫው ተሳታፊነቱን እንደሚያረጋግጥ ኢዴፓ በመግለጫው አስታውቋል፡፡

በዚህ አገር የምርጫ ሥርዓቱ ጠንካራ መሠረት ላይ ሊቆም የሚችለው በማኩረፍና ራስን ከምርጫ ሒደት በማግለል ሳይሆን፣ በሒደቱ ውስጥ በመቆየት ችግሮችንና ጫናዎችን በመቋቋም፣ በማጋለጥና ችግሮች እንዲፈቱ ጥረት በማድረግ ነው ብሎ እንደሚያምንም ኢዴፓ አትቷል፡፡

በዘንድሮ ምርጫ ከሚሳተፉ 58 የፖለቲካ ፓርቲዎች መካከል አንዱ የሆነው ኢዴፓ፣ 165 ዕጩዎችን ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በማቅረብ 501 ዕጩዎችን ካቀረበው የኢትዮጵያ ሕዝቦች አብዮታዊ ዴሞክራሲያዊ ግንባር (ኢሕአዴግ) እና 270 ዕጩዎችን ካስመዘገበው የኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዴሞክራሲያዊ አንድነት መድረክ (መድረክ) በመቀጠል፣ በርካታ ዕጩዎችን በማስመዝገብ ሦስተኛ ፓርቲ መሆኑን የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ መረጃ ያመለክታል፡፡ በቦርዱ መረጃ መሠረት 139 ዕጩዎችን ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በማቅረብ በአራተኛ ደረጃ ላይ የሚገኘው ሰማያዊ ፓርቲ ነው፡፡

The post ኢዴፓ በዕጩዎቹ ላይ እንግልት እየደረሰባቸው ቢሆንም በምርጫው እንደሚገፋ አስታወቀ appeared first on Zehabesha Amharic.

ቆይታ ከዲያቆኑ ሰማዕት ቤተሰቦች ጋር ※ (አዲስ ዜና ነው! በጥሞና ያንብቡት) –ዘመድኩን በቀለ

0
0

endalk
ከሰሜን ተራሮች በራስ ደጀን ተራራ ላይ የሚገኘውን የቅዱስ ያሬድን ገዳም ለእኔና ለበረሃው ጓዴ አብርሃም ዳልሽሃ ደርሶ መልስ 17 ሰዓት ያህል የወሰደብንን የእግር ጉዞ ካደረግን በኋላ ጎንደር በሰላም መግባታችንን ነግሬያችሁ ነበር ።

ጎንደር መዋል ማደሬም ካልቀረ ደግም ለምን ትክልድንጋይ ሄጄ ምንም ቢደክመኝ ለምን በሊብያ የተሰዋው ልጅ ቤት አልሄድም ብዬ ለራሴ ወስኜ ነበር ። ይሁን እንጂ በስዊዘርላንድ የሚኖረውና የቀድሞው ወደገዳማት በምናደርገው ጉዞ ጓደኛዬ የነበረው ጴጥሮስ አሸናፊም ጎንደር ከደረስክ አይቀር እባክህ ተጎጂው ቤት ደርሰህ አሳውቀን የሚለው ውትወታውም አበርትቶኛል ።

ወደዚህ ተጎጂ ቤተሰቦች ዘንድ ለመሄድም ስነሳ ከእኔ ቀድሞ እዚህ ልጅ ወላጅ ቤት ሄዶ የነበረውን አርቲስት ዮሴፍ ገብሬን/ጆሲን/አድራሻ ጠይቄ የስራ ባልደረቦቹ አቶ አባተ እና አቶ ዮሴፍ የሰጡኝን ስልክ ይዤ የሟችን ወንድም በማናገር ቤተሰቦቹ ጋር እንዲወስደኝ ጠየቅሁት።

ወንድምየውም በስልክ እናቴ ወደ ከተማ መምጣት አትችልም እንጂ አባቴን እዚሁ ትክልድንጋይ ድረስ እንደጆሲ ላስመጣልህ ። አንተም ቤተሰቦቼ ያሉት ገጠር ነውና እጅግ አድካሚ ተራራዎችን መውጣትም ይጠበቅብሃልና ግድየለም ከምትደክም አባቴ ትክል ድንጋይ ድረስ ላስመጣው ቢለኝም አይሆንም እዚያው ያሉበት ድረስ ትወስደኛለህ አልኩትና ስልኩን ዘግተን ተለያየን ።

ወርቅ ምድር የዲያቆን እንዳልከው ሐጎስ ቤተሰቦችና ተወልዶ ያደገባት መኖሪያ ቤቱ...

ወርቅ ምድር የዲያቆን እንዳልከው ሐጎስ ቤተሰቦችና ተወልዶ ያደገባት መኖሪያ ቤቱ…

ብዙ በግል ለመሄድ መዘጋጀቴን የነገርኳቸው በጎንደር የሚገኙ ወዳጆቼም አከባቢው አርማጨሆ ስለሆነ እንደው የጸጥታ ችግር ይኖርበት ይሆናልና ገጠር መግባቱን ትተህ ትክል ድንጋይ ድረስ ሂድ ቢሉኝም አለሰማኋቸውም ። ከዚህ ይልቅ እግሬ በስትራፖ ነው የሚባል ተሳስሮ ከአልጋና ደረጃ መውረድ አቅቶኝ ስለነበር እንዴት እራመድ ይሆን ብዬ ነበር ስጋት የያዘኝ ። የሆነው ሆኖ እንድቀር ሺ ምክንያቶች ቢኖሩኝም እና ከፊቴ ቢደረደሩም በጊዜው ለመሄድ ወስኜ ነበርና ወደስፍራው ለመሄድ ተነሳሁ ።

ውድ ጓደኞቼ እንደሰሞኑ ሁሉ ከእኔ ጋር አዋሬ የብርሃኑ ቤተሰብ ጋር ፣ ገርጂ የአያልቅበት እናት እማማ አለሚቱ ጋር ፣ ቂርቆስ የኢያሱ ባለቤት ሮዚና ጋር እንደሄድን ሁሉ ዛሬ ደግሞ ሰሜን ጎንደር በላይ አርማጨሆ ወርቅምድር ቀበሌ ወደሚገኘው የሟች ዲያቆን እንዳልከው ሐጎስ ቤተሰቦች ጋር ልንሄድ ነውና በዓይነ ህሊናችሁ ተከተሉኝ ።

ወደ ሰማዕቱ ቤት ለመሄድ መጀመሪያ ከጎንደር አውቶብስ ተራ ወደ ትክልድንጋይ እንሄዳለን። በመቀጠል ከትክል ድንጋይ ሌላ መኪና እንይዝና ሙሴባምብን አልፈን ኩርቢ የምትባል ከተማ እንደርሳለን ። መኪና ከጎንደር ኩርቢ ድረስ በቀጥታ ይገኛል ይህ የሚሆነው ግን ትክልድንጋይ የሚገኘው የሟች ወንድም ቀደሞ ወርዶ ከጠበቃችሁ ብቻ ነው። ከዚህ በኋላ ግን ከኩርቢ ጀምሮ የተጎጂው ቤተሰቦች ቤት ለመድረስ ወገብን ጠበቅ ማድረግ ነው ከፊት ለፊት የሚገኙትን ተራሮች ለመጋፈጥ ።

ትክልድንጋይ ስደርስ እንዲነግረኝ የጠየኩት አንድ በተሳፈርኩባት ሚኒባስ መኪና ውስጥ አጠገቤ ተቀምጦ የነበረ ወጣት ወዴት እንደምሄድ ምርመራ ቢያበዛብኝ ጊዜ የምሄድበትን ስነግረው ምሳውን ሳይበላ አብሬህ ነው የምሄድ ብሎኝ ተከተለኝ ። የሟችን ወንድም ማቲያስን ከትክልድንጋይ ይዘን ኩርቢ ደርሰን የእግር ጉዞ ጀመርን ። በኩርቢ ከተማ ወጣቱ በሙሉ ይህን ክላሽ እንደ ከዘራ በእጁ ይዞ መታየቱን ባልወደውም ደግነቱ የሟች ወንድምም የሀገሬው ሰው ሰላምታ ሲያበዙለት ማየቴ እንድረጋጋ አድርጎኛል ።
ማትያስ እኔን እና አብሮኝ ድንገት መንገድ የጀመረውን አማኑኤልን ከመንገድ በማቆም ወደ አንዲት ሱቅ በመሄድ አንድ ክላሽንኮቭ እና አንድ ሽጉጥ ይዞ በመምጣት ክላሹን ለራሱ ሽጉጡን አብሮኝ ለመጣው ልጅ ሰጥቶ ጉዞ ጀመርን ።
endalk brother
እኔ እያነከስኩ ማትያስ ስለወንድሙ እያጫወተኝ የበረሃውን መንገድ ተያያዝነው ። በመሳሪያ ታጅቤ መሄዱን ባልወደውም ግን የሀገሩ ባህል ከሆነ ምን ይደረግ ።
መሃል መንገድ ላይ ስንደርስ ሰማዩ ጠቆረ ። ድንገትም ጨላለመ ። ከየት መጣ ያላልነው ዝናብም አንዴ ተዘረገፈብን ። መጠለያ የለ ፣ ወይ ጥላ አልያዝን አማራጩ ከመቆም ወደፊት በዝናቡ እየተወገርን መሄድ ብቻ ነበር ። አሁን እንደምንም በእኔ አካሄድ ወደ 2 ሰዓት የፈጀውን ጉዞ ጨርሰን የሰማዕቱ እንዳልከው ቤተሰቦች መኖሪያ ቤት ጋር ደረስን ።
የሟች ወንድም አስቀድሞ እንግዳ እንደሚመጣ ስለነገራቸው በመጠኑም ቢሆን ጎረቤቶቻቸው ተሰብስበዋል ። ወላጅ አባት የግብርና ሥራቸውን ጀምረዋል የመጡትም ከሥራ ላይ ነው ። እናት ግን ሀዘኑ እስካሁን የለቀቃቸውም አይመስልም ። በጣም በሚያሳዝን ሁኔታ ላይ ይገኛሉ ። ድሮስ እናት እናት አይደለች ። የወለደ አንጀት አይደል የሚባለው ።
ትንሽ አረፍ እንዳልን የመጣሁበትን ምክንያት ተናግሬ ፣ ልቅሶ ለመድረስ ሳይሆን ከሰማዕቱ በረከት ለመቀበል የዚህንም ለማዕተቡ ሲል ዋጋ ይከፈለኝ ወላጆች ለማየት እና ከእናንተም በረከት ለመቀበል የመጣሁ መሆኑን ጭምር በመጥቀስ ጥቂት የማጽናኛ ቃል ከተናገርኩ በኋላ ስለ ልጃቸው እንዲያጫውቱኝ ጠየቅኋቸው ።
እጅግ አድርጎ የግብርናው ስራ እንደጎዳቸው የሚያስታውቁት አቶ ሐጎስ ስለ ልጃቸው እንዲህ ሲሉ በትካዜና አንዳንዴም በቁጭት አጫወቱኝ ። እኔም የሟች ወላጅ አባት ያጫወቱኝን ለእናንተ ለጓደኞቼ በአጭሩ ከብዙ በጥቂቱ እንዲሁ አቀረብኩላችሁ ።

1983 ዓም ጥር 12 ቀን የቃና ዘገሊላ ዕለት የደርግ መንግሥት ይህን ሥፍራ ለቅቆ በምትኩ የኢህአዴግ ሠራዊት አካባቢውን የተቆጣጠረ ዕለት ነበር ህጻን እንዳልክ ሐጎስ ከአባቱ ከአቶ ሐጎስ አየለ እና ከእናቱ ከወይዘሮ የሺእመቤት አስማረ የተወለደው ።

“የበኩር ልጅ የእግዚአብሔር ነው ስለተባልኩ ነፍስ እንዳወቀ በቀጥታ ወስጄ ለየኔታ ኃይለሚካኤል አስረከብኳቸው ። የኔታም በአግባቡ ከፊደል ገበታ ጀምሮ አስፈላጊውን የአብነት ትምህርት አስተምረውት ለክብረ ዲቁና አብቅተውታል ። ልጄም ጎንደር በመሄድ ድቁናውን በመቀበል ከዚህች የገጠር መንደር እስኪወጣ ድረስ በአጥቢያችን በሚገኘው የወርቅ ምድር ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን አገልግሏል ። አቤት ድምጽ አቤት ቅዳሴ ድፍን ሐገር ነበር የሚያፈዝ ። እህህህ ። ኋላ ላይ ወርቅ ምድርን ለቅቆ ትክልድንጋይ ገባ ።
ለምን ? የእኔ ጥያቄ ነበር ።

ይኸውልዎ ከቤተክርስቲያን አገልግሎቱ ጎን ለጎን ዘመናዊ ትምህርቱን እንዲከታተል ስላደረግሁት ዘመናዊ ትምህርቱን ይከታተል ነበር ። በውጤቱም ከክፍሉ ሳይሆን ከአጠቃላይ 1ኛ ነበር የሚወጣ ። በኋላ ላይ የመጀመሪያ ደረጃ ትምህርቱን በወርቅ ምድር እስከ 8ተኛ ክፍል ከተማረ በኋላ ወደ 9ነኛ ክፍል ሲያልፍ በላይ አርማጨሆ ወረዳ በትክልድንጋይ ከፍተኛ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርቱን ለመከታተል ሄደ ። እዚያም ይኸው 10ኛ ክፍል ገብቶ እየተማረ ነበር ። የግማሽ አመቱንም ፈተና ወስዷል እኮ ። ምን ሆኖ ተነስቶ ሄዶ እንዲህ እንደሆነ አላውቅም ። ዝምታ …… ትካዜ ….. ልቅሶ ።

አቶ ሐጎስ ይቀጥላሉ ። ይገርምዎታል ፣ ልጁ ጎበዝ ነው ። እኔ ከአፈር ጋር ስታገል የምኖር አርሶ አደርገበሬ ነኝ ከእጅ ወደ አፍ በሆነችው ኑሮአችን ላይ 6 ልጆችን ወልደናል ። 3 ወንዶችና 3 ሴቶች ። እንግዲህ እሱ አንጋፋ ስለሆነ ተምሮ ከቁምነገር ደርሶ ለተናናሾቹ ብርሃን ይሆናል ብየ ነበር የምጠብቀው ። እኔ ምንም የመርዳት አቅም ስለሌለኝ ራሱን እየረዳ ነበር የሚኖረው ። ከራሱ አልፎ ታናሹን ማትያስን መስመር ለማስያዝ ይጥር ነበር ። ወይ ልጄን ። በአጭር ቀረብኝ እንጂ ።
በመሃል አቶ ሐጎስ ጠየቁኝ ። እኔምሎት ልጄ የሞተው ተርስዎ ልወቅ ብዬ ነው በጥይት ነው ወይስ ከታረዱት ነው ። እሱን ብቻ ይንገሩኝ ።
አይ የእርስዎ ልጅ ከታረዱት ሳይሆን በጥይት ከተገደሉት መሀል ነው አልኳቸው ።

እንዲያስ ከሆነ ደግ ። በጥይትማ እዚህ ታገራችንም ስንቱ ነው ሁል ጊዜ የሚሞት ። አዩ ሀዘኔን ይህ ያቀልልኛል ። መሞቱ ታልቀረ እንደወንዶቹ እንኳንም በጥይት ሆነ ።
ታዲያ ለምን ትምህርቱን አቋርጦ ተሰደደ ? የኔ ጥያቄ ነበር ። ይህን በተመለከተ አባት ምንም አይነት ነገር እንደማያውቁ ፣ ይኽን የሚያውቀው ተሰበሰቡ እንደሆነ እነሱ የልጁን ሞት እንጂ ስደቱን ኋላላይ እንደሰሙ ስለነገሩኝ ቀሪውን ታናሽ ወንድሙ ማትያስ ይነግረናል ።

ማትያስ እንዲህ ይላል ። “ስደትን ከእሱ ከሟች ወንድሜ ቀድሜ የማውቅ እኔ ነኝ በ1995 ወደ ሱዳን ሄጄ ከጥቅምት እስከ ሚያዝያ ድረስ ካርቱም ቆይቻለሁ ። ጨቅጭቆ ጨቅጭቆ አይሆንም ብሎ እየደወለ አባብሎ የመለሰኝ እሱ ነው ። እሱ በመሥራት እና በመማር ነው የሚያምነው ። በትክልድንጋይ በመጀመሪያ ጸጉር ቤት ኋላ ላይ ደግሞ ሞተር ሳይክል ገዝቶ በማከራየት ይኖር ይኖር ነበር።

ድንገት እኮ ነው ተነስቶ ሞተሩን ሽጦ ባህርዳር ሄጄ እስቲ ደግሞ ልሞክር ከፍ ካላሉ ከፍ ማለት የለም ብሎኝ እኔን ብቻ በማማከር ወደ ባህር ዳር የሄደው ። ጥቂት ቆይቶ ደግሞ መተማ ነኝ እዚህ የሚሠራ ሥራ እያጠናሁ ነኝ አለኝ ። ቀጠለና ወደ ሱዳን ልገባ ነው የሆኑ ልጆች አግኝተውኝ ሊቢያ ለምን አትሄድም ብለውኝ ስላሉኝ ልሄድ ነው ። ገንዘቤን በአንተ አካውንት አስገብቻለሁ ። እነሱ ደላሎቹ ገንዘብ ሲጠይቁህ ስጣቸው ብሎ አንዱን ደላላ በስልክ አስተዋወቀኝ ።
እኔም ይሁን ብዬ ሊቢያ የሚገባበትን ቀን መቁጠር ጀመርኩ ። የትንሳዔ ዕለት ከቀኑ 10 ሰዓት ሲሆን ከካርቱም ተነስተናል ልክ የዛሬ ሳምንት ሊቢያ እንገባለን ። ቀሪውን ብርም ያንጊዜ ለደላላው ስጥልኝ ብሎኝ የመጨረሻ ድምጹን ሰምቼ ተለያየን ።
endalk brother
ታዲያ ማረፉን እንዴት ሰማህ ?

ማረፉንማ እንዴት ሰማሁ መሰለህ ። ደላላው ደውሎ ሊቢያ ገብተዋልና ተዘጋጅ ይለኛል ። እኔም መልካም እንግዲያውስ የወንድሜን ድምጽ አሰማኝ አልኩት ። እሱም እሺ ብሎኝ ። ስልኩን ዘጋ ። በከፈተው ጊዜም ስደውል አላነሳ አለኝ ። በኋላ እንዴት ነው ነገሩ ብዬ መተማ ሄጄ የሱዳን ስልክ ገዝቼ ስደውል አነሳልኝ ። እህሳ የወንድሜ ጉዳይስ ስለው ከብዙ ማመንታት በኋላ እንዴት እንደሞተ አትጠይቀኝ እንጂ በሕይወት የለም ሂድና ለቤተሰብህ እርማቸውን እንዲየወጡ አድርግ ። ከአሁን በኋላ ስልኬን ዘግቻለሁ አታገኘኝም ብሎ ስልኩን ዘጋው ። እኔም ያው መጥቼ ቤተሰቡን አረዳሁ ። በቃ ይኸው ነው አለኝ ማትያስ አንገቱን ድፍት አድርጎ በትካዜ ።
አሁን እየመሸ ነው ። የወጣሁትን ዳገት እንዴት እንደምወርድ እያሰብኩ ለመሄድ ተነሳሁ ። እንዳድር ግድ ቢሉኝም መሄድ እንዳለብኝ ነግሬ ተነሳሁ ። አባት አቶ ሐጎስ የእግር ውኃ አምጥተው ደንብ ነው ደግሞም መመለስህ ካልቀረ ይሄን የጓጎለ እግርህን ልሽልህ ብለው ከመሬት ተነጠፉ ። አይደረግም ብዬ እምቢ ብልም የኔ ማጠብ ይቀራል እንጂ ሳትታጠብማ አትሄድም ብለው እግሬን ማትያስ እሽት በማድረግ እንዲያጥበኝ አድርገው የተሳሰረውን እግሬን ፈታ አድርጎልኛል ።
በመቀጠል ለካ ማትያስ እንግዳ እንደሚመጣ ነግሯቸው ነበርና ተዘጋጅተው በፍጥነት የሰሯትን ምግብ አቅርበው ስስት በሌለበት መልኩ መሶብ ሙሉ እንጀራ ድስት ሙሉ ክሽን ያለች የዶሮ ወጥ አቅርበውልን በጉርሻ እያጣደፉ ደስ የሚል ግብዣ አድርገውልን ተመልሰናል ።

እኔም የገበሬ ልጅ ነኝ ። የከተማ ሰዎች አምሮብን ደምቀን የምንኖረው በገበሬ ድካም ነው ። ገበሬ ባይኖርም ምን ይውጠን ነበር ። ገበሬ ደግ ነው ፣ ገበሬ እንግዳ ተቀባይ ነው ። እሱ ከመደቡ ወርዶ መሬት የሚተኛ ። ገበሬ አማኝ ነው ተስፋውን ሁሉ በአምላኩ ላይ አሳርፎ የሚኖር ። አቤት መስተንግዶ ፣ በእውነት ሃዘናቸውን ነው የሚረሱት እንግዳሰው ሲያስተናግዱ ።
የሟች እናትም በዚያ እሾህና ድንጋይ በበዛበት በረሃ ከእንግዲህ እስክሞት ጫማ አላደርግም ብለው የነበረ ቢሆንም ከብዙ ማግባባት በኋላ ጫማቸውን አድርገዋል ።
እነዚህን ሰዎች እንደነገሩኝ ከሆነ ከጆሲ በቀር አንድም የጠየቃቸው እና ያጽናናቸው የለም ። የሀገሬው ሰው ግን ለእንዳልከው እንዳለቀሰ ለማንም እንዳላለቀሰ በአድናቆት ይናገራሉ ።
ከማን ምን እንጠብቅ ?

ይህ የግል ሃሳቤ ነው ። እንደቀደመ ጽሁፌ ሁሉ ባለ ድርሻ አካላት ብዬ ለማስባቸው አካላት መልእክቴን አስተላልፋለሁ ።

በቅድሚያ የክልሉ መንግሥትም ፦ መቼም ይህን ብሔራዊ ሐዘን ምነው አልሰማንም አትሉም ። እንዲህ እንዳትሉ ሀዘኑ የድፍን ሐገር ነው ። እናስ ምነው ምነው ሌላው ቢቀር እኒህን አርሶ አደር ገበሬ ማጽናናት እንዴት አቃታችሁ ። ምኑስ ከበዳችሁ ። እንደክልል መንግሥትነታችሁ ኃላፊነታችሁን ብትወጡ እላለሁ ።

፪ኛው ፦የክልሉ የሚድያ ሰዎች ገጠር ድረስ ሄዶ ዘገባ መስራት ቢያቅታችሁ እንኳን እስከ ኩርቢ ድረስ በመሄድ እኒያን ደካማ ቤተሰቦች ብታጽናኑ ምን ክፋት ይኖረዋል ። በዚያውም የስደትን አስከፊነት ለሌሎች ለማስተማር ይጠቅማችዃል ። እናም እንደእኔ እንደእኔ አንዲት የማጽናኛ ፕሮግራም ብትሰሩ እላለሁ ።

፫ኛ፦ የሰሜን ጎንደር ሀገረስብከት ፦ ይህ የሞተው ልጅ የቤተመቅደሱ አገልጋይ ዲያቆን ነው ። ሲሆን ሲሆን ሊቀጳጳሱ ጭምር ሄደው ቢያጽናኑ ካልተቻለም ደግሞ ቢያንስ ምን አለበት የሀገረ ስብከቱ ሰባክያን ወይም ደግሞ የወረዳው ሰባክያን ሄደው ቢያጽናኑ ። አሁንም አልረፈደም የ40ኛ ቀን መታሰቢያው እየደረሰ ስለሆነ አስቡበት ።
፬ኛ ፦ የጎንደርና የአካባቢው መንፈሳውያን ማኅበራት ፦ መቼም እናንተን በኅብረታችሁ ፣ በመንፈሳዊ ህይወታችሁ የማይቀና ኢትዮጵያዊ የለም ። በአክሱም ፣ በላሊበላና በግሸን እንዲሁም በጣና ክርስቶስ ሠምራ ገዳም የምታደርጉት መንፈሳዊ እንቅስቃሴ ይታወቃል ። ከሁሉ በላይ የጥምቀትን በዓል ልዩ የሆነ መንፈሳዊ ድባብ እንዲኖረው ማድረጋችሁ ይታወቃል እናም እዚህ ከአፍንጫችሁ ሥር ባለ ታሪክ ላይም እንድትረባረቡ እጠቁማችሀለሁ ። በተለይ ሰማዕቱ ቀድሶ ያደገባትን የወርቅ ምድር ቅዱስ ሚካኤልን ቤተክርስቲያን ሄዳችሁ በረከትን ተቀበሉ ።

፬ኛ ፦ እኛ ደግሞ በተቻለን አቅም በሐገር ውስጥም ሆነ ከሐገር ውጭ ያለን ኢትዮጵያውያን የተቻለንን ከቁርሳችንም ቢሆን ቀንሰን ብንረዳቸው በህይወት ያሉትን በትምህርት ራሳቸውን የሚችሉበትን ዘዴ በ ንፈልግላቸው መልካም ነው ።

እኔ ወደ ጎንደር መኪና በመጥፋቱ ከኩርቢ ለ3 በአንድ ሞተር ላይ ሦስታችን ከትክልድንጋይ ጎንደር ድረስ ደግሞ እኔና ባለሞተርሳይክሉ ብቻችንን በዚያ ጨለማ በየቦታው ፍተሻ እያደረግነ አሁን ከማረፊያዬ ገብቻለሁ ። በፕሮግራሜ መሰረትም ዛሬ እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ ወደቤተሰቤ እመለሳለሁ ። አብርሃምም የጎን አጥንት መሰንጠቅ እንደገጠመው ተነግሮት በመልካም ሁኔታ ላይ ይገኛል ።

“የረዳኸኝ ብርታትና ጥንካሬንም የሰጠኸኝ አምላኬ ሆይ ! ተመስገንልኝ “።
“ድንግል ሆይ እናቴ ! ዛሬም እንደትናንቱ ቅደሚ ከፊት ከኋላዬ ” አሜን
በተረፈ እኔ ከስንቄ የተረፈኝን ሳንቲም እና ወደዚያ እየሄድኩ መሆኔን በአጋጣሚ ሰምታ የነበረች እህቴ በዚያው ከአንተ ስጥልኝ ባለችኝ መሠረት ሰጥቻለሁ ። ቤተሰብ ለሚላኩ ብሮች ከተማ ድረስ መምጣት ስለማይችሉ ጆሲ የሰጠው ብር ጭምር በታናሽ ልጃቸው ስም በባንክ የተቀመጠ በመሆኑ በዚያው ባንክ ቁጥር አስገቡላቸው ።
ማትያስ ሐጎስ አየለ
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
ትክልድንጋይ ቅርንጫፍ
የባንክ ሒሳብ ቁጥር
833501000418 ነው ።
ስልክ ቁጥር + 251934527249 ማትያስ ብላችሁ ደውሉለት ።
ዘመድኩን በቀለ ነኝ
ግንቦት 13/9/2007 ዓም
ጎንደር— ኢትዮጵያ

The post ቆይታ ከዲያቆኑ ሰማዕት ቤተሰቦች ጋር ※ (አዲስ ዜና ነው! በጥሞና ያንብቡት) – ዘመድኩን በቀለ appeared first on Zehabesha Amharic.

Viewing all 15006 articles
Browse latest View live