Quantcast
Channel: Ethiopian News | ዘ-ሐበሻ | Latest News Provider | News For All
Viewing all 15006 articles
Browse latest View live

የ9ኙ ፓርቲዎች ትብብር የትግል ጥሪ አስተላለፈ

$
0
0

በነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተር

10304784_666160690176259_2094795952727390569_nየ9ኙ የተቃዋሚ ፓርቲዎች ትብብር ‹‹ነጻነት ለፍትሃዊ ምርጫ›› በሚል መርህ የሁለተኛ ዙር የሠላማዊ ትግል ጥሪውን ለተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች አስተላለፈ፡፡ ትብብሩ የካቲት 15 ቀን 2007 ዓ.ም በተመሳሳይ ሰዓት በ15 ከተሞች ሊያደርገው አቅዶት የነበረውን ሰላማዊ ሰልፍ በሳምንት አራዝሞ ለየካቲት 22 ቀን 2007 ዓ.ም ማስተላለፉንም አስታውቋል፡፡

ትብብሩ ዛሬ የካቲት 10 ቀን 2007 ዓ.ም በሰማያዊ ፓርቲ ጽ/ቤት በሰጣው ጋዜጣዊ መግለጫ እንዳስታወቀው፣ ገዢው ፓርቲ የቱንም ያህል አሰቃቂና አረመኔያዊ የአፈና እርምጃዎች ቢወስድም የህዝብ ጥያቄዎች እስካልተመለሱ ድረስ ህዝባዊ ትግሉን ማዳፈን እንጂ ማስቆም እንደማይችል ይልቁንም ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ከተለያዩ የህዝብ እንቅስቃሴዎች መገንዘቡን ገልጹዋል፡፡ ትብብሩ ምርጫን በተመለከተ እንዳስታወቀው ኢህአዴግ ስለመድብለ ፓርቲ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ከቃላት ያለፈ እምነትም ሆነ ቁርጠኝነት የሌለው መሆኑን በዚህ የምርጫ ወቅት በተፎካካሪ ፓርቲዎች ላይ እየወሰደ ያለው ህገ-ወጥ እርምጃ ማሳያ ነው ብሏል፡፡

‹‹ለውጡ የሚመጣባቸው አምባገነኖች ድንገተኛ ከፍተኛ ፍርኃትና ሥጋት በማሳደሩ ህገ-መንግሥቱን በመጨፍለቅ በግልጽና በአደባባይ ህገ-ወጥ ውሳኔዎችንና እርምጃዎችን ለመውሰድ መገደዳቸው፣ ይህም የህዝቡን የለውጥ ፍላጎትና የትግል ተነሳሽነት በማሳደግ ህዝባዊውን ትግል ወደ ላቀ ደረጃ ማሸጋገሩ የበለጠ ግልጽ ሆኗል›› ብሏል ትብብሩ፡፡

ትብብሩ አሁን ባለንበት ተጨባጭ ሁኔታ የአገራችንና ዜጓቿ ቀጣይ ዕጣ ፈንታ በሁለት አማራጮች ላይ የተንጠለጠለ ነው ያለው መግለጫው፣ አንድም ያለውን አምባገነናዊ ሥርዓት ተቀብሎ የጭቆና ቀንበር ተሸክሞ በከፋ ውርደት ሥር ሰጥ- ለጥ ብሎ መገዛት፣ አሊያም አምባገነንነትና ጭቆናን ‹‹በቃ›› በማለት በሕዝባዊ የተቀናጀ ሰላማዊ ትግል ለአገራችን ሉዓላዊነትና የዜግነት ክብራችንን ለማስመለስ በህገ መንግስታዊ መብታችን ተጠቅመን ትግላችንን እስከማይቀረው ለውጥ ድል ደጃፍ ድረስ በቆራጥነት መቀጠል ናቸው ብሏል፡፡

በዚህም ትብብሩ ህገ-መንግስታዊ መብትን በመጠቀም በህግና በሥርዓት ትግሉን ለመምራት መዘጋጀቱን በመግለጽ፣ የተለያዩ የህብረተሰብ ክፍሎች የትግል ጥሪውን እንዲቀላቀሉት አሳስቧል፡፡ ስለሆነም ትብብሩ ‹‹ኢህአዴግነት ከዜግነት በላይ›› ለሆነባቸው የሥራ ዋስትናቸው፣ ዕድገትም ሆነ ሌሎች ጥቅማ ጥቅሞች በሙያቸው፣ በልምዳቸው፣ ክህሎታቸው፣ በመሳሰሉት ባልተመሰረተ መልኩ በደል እየደረሰባቸው ላሉ ሁሉ የትግል ጥሪውን አስተላልፏል፡፡

‹‹የህወኃት/ኢህአዴግ ተራ አባላትና ካድሬዎች፤ የፖለቲካ ልዩነት የተለያየ አመለካከትና ሀሳብ ማራመድ ጤናማ የመድብለ ፓርቲ ፖለቲካ መገለጫ እንጂ እንደሚነገራችሁ ‹‹ጠላትነት›› ባለመሆኑ፣ ትግላችንም ለሠላማዊና ህጋዊ የሥልጣን ሽግግር እንጂ በናንተ ‹‹መቃብር›› ላይ አዲሱን ሥርዓት የማቆም፣ የነበረውን አጥፍቶ ከዜሮ የመጀመርና እናንተን የማጥፋት ዓላማ እንደሌለው ተረድታችሁ፣ ተቃዋሚዎች እንደናንተው ኢትዮጵያዊያንና ለኢትዮጵያና ህዝቧ የሚጨነቁ መሆናቸውን በመረዳት ተቃዋሚዎችን እንደ‹‹ ጠላት›› ከመመልከት አስተሳሰብ ራሳችሁን ነጻ እንድታወጡ›› ሲልም ትብብሩ መልዕክቱን አስተላልፏል፡፡

ወጣቶችና ሴቶች በተለይም የወጣቶችና ሴቶች አደረጃጀቶች፣ መምህራንና ተማሪዎች በተለይም የዩኒቨርስቲና የሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎች፣ የእምነት ነጻነት መብት ጠያቂ የማኅበረሰብ አባላት፣ የመገናኛ ብዙሃን አባላት፣ የፍትህ አካላት፣ የዴሞክራቲክ ፓርቲዎች አባላት፣ የነጻነትና የዴሞክራሲ ሰላማዊ ታጋዮች፣ በውጪ አገር የሚኖሩ ኢትዮጵዊያን/ዲያስፖራዎች እና ሌሎችም ጥሪው የተላለፈላቸው አካላት መሆናቸውን መግለጫው አትቷል፡፡

በመሆኑም፣ ‹‹በምናርገው አገራዊ፣ ሰላማዊና ሕዝባዊ ትግል በማይቀረው የሥርዓት ለውጥ ለሰላማዊ የሥልጣን ሽግግር በአንድነትና በቆራጥነት እንድትሰለፉ፤ የካቲት 22/07 በየከተሞቹ በቦታውና በሰዓቱ እንድትገኙ ጥሪያችንን አበክረን እናቀርባለን›› ብሏል የ9ኙ ፓርቲዎች ትብብር፡፡

The post የ9ኙ ፓርቲዎች ትብብር የትግል ጥሪ አስተላለፈ appeared first on Zehabesha Amharic.


ለ11 ሰዎች ሰዎች መጥፋት ምክንያት የሆነው የሲኖ ትራክ እና የሚኒባሱ ግጭትና የተቃጠሉበት ፎቶዎች ይዘናል

$
0
0

ዘ-ሐበሻ ጠዋት ላይ በቡራዩ ከተማ አስተዳደር ወረዳ ሁለት ልዩ ስሙ ቀርሳ በተባለ ስፈራ ትላንት ማምሻውን በደረሰ የትራፊክ አደጋ የ11 ሰው ህይወት ሲያልፍ ሁለት ሰው ላይ ከባድ ጉዳት በሚል ዘግባ ነበር:: አደጋው የደረሰው ትላንት ምሽት 1 ሰዓት ከ20 ደቂቃ ላይ ሲሆን፥ ወደ አዲስ አበባ ይመጣ የነበረ ሲኖ ትራክ የጭነት ተሽከርካሪ ከሚኒባስ ጋር በመጋጨቱ አደጋው መድረሱን መዘገባችን ይታወሳል:: የታጋጩትና የተቃጠሉትን የሁለቱን መኪናዎች ሁኔታ የሚያሳይ ፎቲ ግራፎች ከአዳነ አረጋ አግኝተናል – ይመልከቱት:-
kataelo

katelo 2

katelo 3

The post ለ11 ሰዎች ሰዎች መጥፋት ምክንያት የሆነው የሲኖ ትራክ እና የሚኒባሱ ግጭትና የተቃጠሉበት ፎቶዎች ይዘናል appeared first on Zehabesha Amharic.

የደቡብ አፍሪካዊያን ዕዳ! –ሠዓሊ አምሳሉ ገ/ኪዳን አርጋው

$
0
0

ethiopian-in-south-africa

የማንዴላ ልጆች ወገኖቹ ፤ የዋልንላቸው ውለታ
ይህች አፍሪካ በነጻነት ፤ እንድታገኝ እፎይታ
ጥረታችን ሁሉ ሰምሮ ፤ አገኙና ነጻነት
በእኛ ቀን ሲዘነብል ፤ ብንሔድባቸው ስደት
ከቅኝግዛት እስከ አፓርታይድ ፤ የረገጣቸው እያለ
ወንድም ጓዱን ሐበሻ ፤ ስለ እሱ ዋጋ የከፈለ
ከሀገር ይውጣ ብሎ ጮኸ ፤ ጎዳናው ላይ እያቃጠለ፡፡
ምንነው ወገኔ ምን ነው? ፤ አእምሮም የለህ ማሰቢያ?
ምን እንደሆነች አታውቅም? ፤ ውዷ የኔ ሀገር ኢትዮጵያ?
በከፈልንላቹህ ዋጋ ፤ በእናን ተየተነሣ
እንዲህ ሆና እንደቀረች ፤ በነጫጭ ጅቦች ተነክሳ?
ታወክን ታመስን እንጅ ፤ በነጭ ሰይጣናት እከይ
ወደ እናንተ የተመምነው ፤ መች አጥተን ነበር ሲሳይ
ስለ እናንተ ባደረግነው ፤ ከዲፕሎማሲው ማሳደም
መሪዎችህን አሠልጥኖ ፤ በግንባር እስከ ማፋለም
በእኛ ጥረት ነበርና ፤ ነጻነትህ የተገኘ
ጥርስ ነከሱ በእኛ ላይ ፤ ልባቸው በቀል ተቃኘ
እርስ በርሳችን ብንባላ ፤ እንድንሆን ከንቱ መና
ያለ እነሱ ማንም የለም ፤ የሴራው ምንጭ ሲጠና
ላንተ ስንል በከፈል ነው ፤ ለዚህ ብንበቃ ብናጣ
ማስጠጋት ሲገባህ በክብር ፤ የጠላትህን ባላንጣ
የክፉ ቀንህን አጋር ፤ የተሰጠህን ዕጣ
እሳት በላዩ እየለቀክ ፤ ማባረሩ ነው የሱ ዋጋ?
ከቶ በምን ሒሳብ ነው? ፤ ሕሊናም የለ አንተ ጋ?
ፍዳ ያስቆጠረህ ባዕዱ ፤ እየኖረ ተንቀባሮ
ላንተም ኢምንት ያልከፈለው ፤ መጥቶ ከህንድ ተሻግሮ
በምቾት ድሎት እየኖረ ፤ ሞጃ ሆኖ ገኖ ከብሮ
በገዛ የራስ ሀገርህ፤ አንተን ባዶ አርጎ ገፍትሮ
የገዛ ሀገርክን ከተማ ፤ እያስቋመጠህ አማልሎ
ነጻነትህ ትርጉም አጥቶ ፤ ገብተህ ለመርገጥ ከልክሎ
ይሄ ሳያምህ ሳይቆጭህ ፤ ወኔህተሰልቦ ተገሎ
ሀሞትህ ፈሶ ፈራርሶ ፤ ጉልበትህ ከድቶህ ሰልሎ
ይሄንን የሚያህል ውርደት ፤ ተሸክመኸው እያለ
በዚህ ዘመን አሁን ዛሬ ፤ ነጻ ነኝ እያልክ ታደለ
ምስኪኑ ደሀው ወንድምህ ፤ ምን አረገ? ምን በደለ?
ያንተን ቀንበር ተሸክሞ ፤ በሞተልህ በቆሰለ?
ሀገሬን ካልክ መብቴን ፤ የራሴን ሀብት እንጀራ
የወሰደብህ እያለ ፤ ድልቡን ዋናውን ጎተራ
ፍርፋሪውን ለቃሚው ፤ ወንድም ሐበሻው ምን ሠራ?
እንዴት ነው እሱ ነገሩ ፤ የባሕል ወጋቹህ ዕይታ?

ጠላትን ከወዳጅ መለያው ፤ ብድር ለመክፈል ውለታ
ተገላቢጦሽ ነው እንዴ? ፤ ለወዳጅ ክፉን መልሶ
ዘርፎ እራቁቱን ማስቀረት ፤ ካገር ማባረር አስለቅሶ?
ገድሎ መንገድ ላይ መጎተት? ፤ መልካም ምግባሩን አርክሶ?
መልካሙን ለጠላት በማቅረብ ፤ ባርነትን መኖር መልሶ?
ይሄ ነው ባሕል ወጋቹህ? ፤ የማሰብ ልካቹህ ተሐድሶ?
እኛ እኮ እንደዚያ የደከምን ፤ ከዲፕሎማሲም ኃይል እርዳታ
እንድትኖሩ አልነበረም ፤ በእንደዚህ ዓይነት ሁኔታ
ወይ ከዳር ደርሶ አላየን ፤ የነጻነቱን ፍልሚያ
ድካማችንን ከንቱ አረገው ፤ ዛሬ ያለብህ ግሊያ
እንዲህ በአድሎ እየኖርክ ፤ ከማዶ ከኬላ ወዲያ
አፓርታይድ የለም ትላለህ? ፤ በዚህ አናፍርም ታዲያ?
ዕያየነው በመሆኑ፤ ዛሬም ሆናቹህ ባሪያ

ለማይሆን ነገር በከንቱ ፤ ብናስገኝ ላይ ታች ሮጠን

ነጻነትህን አልኖርከው ፤ ለእኛ ነው ቂሙ የተረፈን፡፡
ወገኔ ማጥፋት ማስወገድ ፤ ድል ማድረግ ያለብህ እኮ
ይሄንን ውርደትህን ነው ፤ ያስቀረህን አንበርክኮ
ሀገርህን ማስመለስ ነው ፤ ከተወሰደብህ ምርኮ፡፡
የኔስ ግምት የነበረው ፤ ወገኔ ሆኖ ስደተኛ
ወዳገርህ ሲጎርፍ ሲተም ፤ ሆኖ ሊኖር ጥገኛ
ያለውን ህልም ያውቃሉና ፤ ዓላማ ምኞቱን ለአንተ
የፈራሁ ነጮቹን ነበር ፤ ግምት ሥጋቴ ሳተ
ጭራሽማ እዚህ ገብቶ ፤ አብሮ ሆኖ እየኖረ
በምክር እያነሣሣ ፤ ገፋፍቶ እያዳፈረ
መፈጸሙ አይቀር ብለው ፤ የቀረውን የቤት ሥራ
ያነቃብናል ዋ! ኋላ ፤ መንገድ ጠቁሞ እየመራ
አይሆንም ሐበሻ ይውጣ ፤ ብየ እንዳያሴሩ ሴራ
እንጅ እናንተማ እንደምን? ፤ እኮ እንዴት ብየ ጠርጥሬ?
ወንድም ነው ዕዳም አለበት ፤ ባልኩት እንዳይን አሳሬ፡፡
ግን ምንም ያለህ አልነበረም ፤ እሱ አባትህ ማንዴላ
ዕዳ አለብን አላለህም? ፤ ያንን ዕዳ እንዳትበላ?
ወይስ ነው ችግሩ ያንተ? ፤ ቃሉን ያልሰማህ አደራ?
ማዲባዬ እያልክ አባቴ ፤ የነጻነት ታጋይ አውራ
ኧረ ተው አባትክን ስማ ፤ ሰምተናል ብዙ እንዳለ
ጠብቅ እንጅ ቃል አደራን ፤ ምን ነው? በማን ተማለ?
ይሄንን ቃል ባትሰማ ፤ በሰማይ ባንተ ፍርድ አለ!
ሠዓሊ አምሳሉ ገ/ኪዳን አርጋው
ጥር 19 2007ዓ.ም.

 

The post የደቡብ አፍሪካዊያን ዕዳ! – ሠዓሊ አምሳሉ ገ/ኪዳን አርጋው appeared first on Zehabesha Amharic.

ምን እየጠበቅን ነው? «የትግራይ ሪፑብሊክ ድንበር አል-ወሃ ድረስ ነው» –ሞረሽ ወገኔ የዐማራ ድርጅት

$
0
0

ማክሰኞ የካቲት ፲፩ ቀን ፪ሺህ፯ ዓ.ም. ቅፅ ፫ ፣ ቁጥር ፲፩

የትግሬ ወያኔ በኃሣብ፣ በዕቅድ እና በተግባር ፀረ-ዐማራ፣ ፀረ-ኢትዮጵያ እና ፀረ-ኢትዮጵያዊ የሆነ ድርጅት መሆኑን ከተፈጠረበት ጊዜ ጀምሮ ያረጋገጠው ሃቅ ነው። ሠሞኑንም ከመገናኛ ብዙሃን የሚደመጠው «የትግራይ ድንበር አል-ውሃ ድረስ ነው» የሚለው ወሬ የዚሁ የሚጠበቀው የትግሬ-ወያኔ ተከታይ እርምጃ እንደሆነ አያጠያይቅም።
R_of_Tigrai
ኢትዮጵያን የማፈራረሱ የንድፈ-ኃሣብ መሠረት የተጣለው በተለያዩ የውጭ ኃይሎች እንደሆነ ይታወቃል። ከእነዚህ መካከል ሮማን ፕሮቻዝካ የተባለው የኦስትርያ-ሐንጋሪ መሥፍን (Baron Roman Prochazka) ወጥነት ባለው መንገድ አዘጋጅቶ ያሠራጨው መጽሐፍ ዋና ተጠቃሽ ነው። የሮማን ፕሮቻዝካ መጽሐፍ ኢትዮጵያ በፋሽስት ጣሊያን በተወረረችበት በ፲፱፻፳፰ ዓ.ም. (1935 G.C.) በጀርመንኛ ቋንቋ «Abessinien: die schwarze Gefahr» በሚል ርዕስ፣ በኋላም በ1935 G.C. ወደ እንግሊዘኛ ተተርጉሞ «Abyssinia: The Powder Barrel» ተብሎ ወጥቷል። መጽሐፉ፣ በተለይም ዐማራውን፣ «የነጮችን የበላይነት የማይቀበል፣ ሌሎችን ነገዶች እና ጎሣዎች ጨቁኖ እና ረግጦ የሚገዛ» እና አልፎ ተርፎም «ኢትዮጵያን በአውሮፓውያን የቅኝ ግዛት ሥር እንዳትውል የሚያደርግ ቀንደኛ ጠላታቸው» እንደሆነ ያትታል። ሮማን ፕሮቻዝካ ባቀረበው የመፍትሔ ኃሣብ በግልጽ እንዳሠፈረው፣ ኢትዮጵያን ለማዳከም እና ለማፈራረስ በቅድሚያ የሥልጣን ምንጭ እና የአንድነት ምልክት የሆነውን ዘውዳዊ ሥርዓት መገርሰስ፤ የሕዝቡ መንፈሣዊ ሕይዎት የበላይ እና የዘውዳዊ ሥርዓቱ ርዕዮተ ዓለማዊ ክንድ የሆነችውን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያንን ማዳከም እና ማጥፋት፣ እንዲሁም ራሱን በቋንቋ ክልል ያላደራጀ፣ በሠፊዋ ኢትዮጵያ ተሰራጭቶ የሚኖር የኢትዮጵያዊነት ብሔርተኝነት አቀንቃኝ የሆነውን የዐማራው ነገድ መጥፋት እንዳለባቸው ለፀረ-ኢትዮጵያ ኃይሎች ምክር ይለግሣል። የፋሽስት ጣሊያን መሪ የነበረው ሞሶሎኒም ሆነ የትግሬ-ወያኔ ያስፈጸሙት እና የሚያስፈጽሙት ይህንኑ ነው።

ፋሽስት ሞሶሎኒ ለ፭(አምስት) ዓመታት ከኢትዮጵያ አርበኞች የሚደርስበትን ጥቃት እየተከላከለ፣ በኢትዮጵያ ከተሞች ዙሪያ በቆየበት ወቅት ያከናወናቸው ተግባሮች የሮማን ፕሮቻዝካን ምክር ተከትሎ ነበር። በቅድሚያ ለ፫(ሦሥት) ሺህ ዘመናት የዘለቀውን ዘውዳዊ ሥርዓት አፍርሶ ኢትዮጵያን በይፋ የኢጣሊያው ንጉሥ ኢምቤርቶ ግዛት ተቀጥላ አደረጋት። የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ኃይማኖትን በልዩ ልዩ መንገዶች አዳከመ። የአገሪቱን አስተዳደራዊ ክልል ቋንቋን መሠረት ባደረገ በ፮(ስድስት) ከፋፍሎ አደራጀ። «ዐማራ» ብሎ ከከለለው ግዛቱ ውጭ የሚኖሩ ዐማሮችን ዛሬ የትግሬ-ወያኔ እንደሚያደርገው አባረረ። «ጋላ ሲዳማ» ብሎ ዋና ከተማውን ጅማ ላይ አድርጎት በነበረው ግዛት ከ80,000 (ሰማኒያ ሺ) በላይ ዐማሮችን አባሯል። ልክ ዛሬ የትግሬ-ወያኔ በሚያደርገው መልኩ የአማርኛ ቋንቋ ከዐማራ ክልል ውጭ እንዳይነገር አድርጎ ነበር፣ ወዘተርፈ። በተመሣሣይ ሁኔታም የትግሬ-ወያኔ በቁጥር ከ፭(አምሥት) ሚሊዮን የማያንሱ ዐማሮች ገድሏል። «የዐማራ ክልል» ብሎ ከከለለው ግዛት ሣይቀር በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ዐማሮችን «አገራችሁ አይደለም» ብሎ አባሯል። የዐማርኛ ቋንቋን ለማጥፋት ሠፊ ዘመቻ ከፍቷል።

የትግሬ-ወያኔ ኢትዮጵያን የማፈራረሱ ዓላማው የሠከነ እንዲሆን ከሠራቸው መሠሪ ዋና ዋናዎቹ ሥራዎች መካከል «ሕገ መንግሥት» ብሎ ባዘጋጀው ሕገ-አራዊት በአንቀፅ 1፣ 2፣ 39 እና 50-52 ያሠፈራቸው ናቸው።

አንቀጽ 1፦ «እኛ የኢትዮጵያ ብሔር/ብሔረሰቦች ሕዝቦች ….» ሲል ነው የሚጀምረው። ይህም አንድ ኢትዮጵያዊ ነኝ የሚል ዜጋ ወይም ሕዝብ እንዳይኖር፣ ሁሉም በነገዱ ዙሪያ ብቻ ተሰባስቦ ኢትዮጵያዊነትን አውልቆ እንዲጥል ከታለመ የሩቅ ግብ አኳያ የተቀመረ ለመሆኑ ማንም አይስተውም። ቀመሩም የኢትዮጵያ ማፍረሻ መሆኑን አንድ በሉ። በዓለም ላይ የሚገኙት ነገዶች እና ጎሣዎች ሁሉ ተቀላቅለው በሚኖሩባት አሜሪካ፣ በርካታ ጎሣዎችን ባቀፉት ቻይና እና ሕንድ፣ ወዘተርፈ በሕገ-መንግሥታቸው «ሕዝብ» እንጂ «ሕዝቦች» አይሉም። በአንድ ሕገ-መንግሥት ሥር የሚተዳደር ሕዝብ፣ «ሕዝብ» እንጂ «ሕዝቦች» ተብሎ አይጠራም።

አንቀጽ 2፦ «የኢትዮጵያ ወሰን የብሔር /ብሔረሰቦቿ ወሰን ነው» ይላል። የኢትዮጵያ ዳር ድንበር በታወቁትና ዓለም በተቀበላቸው ቋሚ የድንበር መለያዎች የተቀመጠ አይደለም። የትግሬ-ወያኔ «ኢትዮጵያዊ መንግሥት» ሆኖ ለመዝለቅ ቢያስብና ፍላጎቱ ቢኖረው ኖሮ ይህን አንቀጽ በዚህ መልክ አያስቀምጠውም ነበር። በምትኩ በአንቀጹ ሊቀመጥ የሚገባው፦ «የኢትዮጵያ ወሰን በዓለም አቀፍ ስምምነቶች መሠረት ዕውቅና ባገኘውና በካርታ ላይም ከምድር ወገብ በስተሰሜን ከ-እስከ ዲግሪ፣ ከግሪንዊች ሜሪዲያን ወደ ምሥራቅ ከ-እስከ ዲግሪ» ተብሎ መሆን ነበረበት። ይህን ግን እንዲሆን አልተፈለገም። ምክንያቱም እነዚህ ቋሚ መስፈርቶች ከተቀመጡ ሕዝቡ የአገሩን ወርድና ቁመት ሊያውቅ ነው። ወያኔ እየሸራረፈ ለፈለገው አካል የሚሰጠው መሬት «ለምን?» ሊባል ነው።

አንቀፅ 39 (1)፦ «ማንኛውም የኢትዮጵያ ብሔር፣ ብሔረሰብ፣ ሕዝብ የራሱን ዕድል በራሱ የመወሰን እስከ መገንጠል ያለው መብቱ በማናቸውም መልኩ ያለገደብ የተጠበቀ ነው።» ይላል። ይህ ምን ማለት ነው? ትግራይ፣ ኦሮሚያ፣ ሶማሊ፣ ጋምቤላ፣ ወዘተርፈ ተብለው የተፈጠሩት አዳዲስ የባንቱስታን ግዛቶች በሕገ አራዊቱ አንቀጽ 39 በተሰጣቸው መብት መሠረት «በኢትዮጵያ ሥር አንቀጥልም፣ አብሮነት አንሻም፣ እንገነጠላለን» ካሉ የእነዚህ ክልሎች «ዜጋ» ከሚባለው ውጪ እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ በጉዳዩ ላይ ድምፅ የማሰማት መብት የለውም ማለት ነው። በእርግጥ የዚህ አንቀጽ በሕገ-አራዊቱ መካተት ተጠቃሚ ማንም ሣይሆን የትግሬ-ወያኔ ብቻ ነው። ምክንያቱም የመገንጠል ጥያቄ የሚያነሱ ሌሎች ኃይሎች ለግንጠላው ማሟላት የሚገባቸውን ጉዳዮች በቀላሉ ማሟላት አይችሉም። እያንዳንዱ ክልልም ለይስሙላ በራሱ ክልል ተወላጅ የሚገዛ ቢሆንም፣ እኒህ አሻንጉሊት ገዢዎች ከትግሬ-ወያኔ ፍላጎት ውጭ ምንም ነገር ማድረግ አይችሉም። ስለዚህ የዚህ አንቀጽ ዋና ዓላማ ወደፊት የምትመሠረተዋን የትግራይ-ትግሪኝ ሪፑብሊክን ለመመሥረት «ሕጋዊ መሠረት» ለመስጠት መሆኑ ሊታወቅ ይገባል።

ከአንቀጽ 50-52፦ የሥልጣን መዋቅሩን የሚያመለክቱ አንቀጾች ናቸው። በእኒህ አንቀጾች እንደተጠቀሰው ከፍተኛ የሆነው እና በአገሪቱ ዕጣ ፈንታ ላይ የመወሰን ሥልጣን ባለቤት ያለው «ፓርላማ» ተብዬው ነው። ሆኖም በተግባር የሚታየው ሃቅ ግን በኢትዮጵያ ከፍተኛውን ሥልጣን የያዘው «ፓርላማው» ሣይሆን፣ በሕወሓት ሥራ አስፈጻሚ እና ማዕከላዊ ኮሚቴዎች በአምባገነንነት ተጨምድዶ የተያዘ መሆኑን ነው። ስለሆነም፥ ፓርላማ፣ የሚኒስትሮች ምክር ቤት እና ኢሕአዴግ የሚባሉት መዋቅሮች የተሞሉት የትግሬ-ወያኔ ፖሊት ቢሮ አባላት ወስነው የሰጡዋቸውን «ለምን? እንዴት?» ሣይሉ በሚያስፈጽሙ ታዛዥ አሽከሮች ነው።

በሌላ በኩል የትግራይ ግንጠላ የማይቀር እና የትግራይ-ትግሪኝ ሪፑብሊክ ምሥረታ ሁኔታ እየተመቻቸ እና የማይቀር መሆኑን በቅርቡ ፕሮፌሰር ተስፋጽዮን መድኃኔ የተባሉ « ይኸውና! ኤርትራ ሞተች። ትግል ለሀገር ትንሣዔ!» በሚል ርዕስ በጻፉት መጽሐፍ አያሌ ማስረጃዎችን በመዘርዘር ግልጽ ኣድርገውታል። ፕሮፌሰር ተስፋጽዮን የትግሬ-ወያኔ የትግራይ-ትግሪኝ ምሥረታ ዕውን ለማድረግ እየሠራ እንደሆነ የሚከተሉትን ማስረጃዎች ይጠቅሳሉ።

ሜንሆት ወልደማርያምን በመጥቀስ «ሕወሓት የትግራይ ነፃ ሀገር ኅልውና ለማመቻቸት ሲል የብሔር ብሔረሰቦች የራስን ዕድል በራስ መወሰን እስከ መገንጠል የሚል መሠረት ድንጋይ አስቀምጧል። ይህም በሀገሪቱ የጸደቀውን (ኤትኒክ ፌዴራሊዝም) መሠረት ባደረገው ሕገመንግሥት የተደገፈና የታቀፈ እንዲሆን ተደርጓል። ትልቁ ዓላማም ሀገረ ትግራይን ለማቋቋም አንዳንድ የኤርትራ ቦታዎችን ቆርሶ ወደ ትግራይ ማካለል ነው።»( ገጽ 12)

«አቶ ስብሐት የባድመ ቀውስ ትልቅ መነጋገሪያ ሆኖ፣ ኢሣያስ ሰላማዊ መፍትሔ አልቀበልም ብሎ አፈንግጦ በነበረበት ጊዜ፣ ኢትዮጵያ በኤርትራ ላይ የኃይል ርምጃ እንዳትወስድ የሚቻለውን ያህል አድርጎ ነበር። አሁንም ቢሆን ኢትዮጵያ ከኤርትራ ጋር መዋጋት አልነበረባትም ባይ ነው። የአቶ ስብሐት ነጋ አቋም መነሻው የኤርትራና የትግራይ ዝምድና ሕያው ነው የሚል አመለካከት ነው። አቶ ስብሐት «ትግራይ እኮ ካለ ኤርትራ አትኖርም፣ ኤርትራም እንደዚሁ» (ገጽ 13) የሚለው አክራሪ እምነቱ የትግራይ መገንጠል አይቀሬነት የሚያመልክት አቋም እንደሆነ ጸሐፊው ያምናሉ። ይህ የስብሐት አቋም ወይም አባባል ደግሞ ዝም ብሎ ለማለት ያህል የተባለ ሳይሆን፣ ከመለስ ሞት በኋላ በወያኔ መሪዎች አካባቢ የትግራይ መገንጠል እና ከኤርትራ ጋር ሊኖራት የሚችል ዝምድናን በሚመለከት ውስጥ ለውስጥ እየተካሄደ ያለው መመሣጠር መገለጫ መሆኑን ያስረዳል።

«ወያኔ ወይም አመዛኙ የአመራር ክፍል በኢትዮጵያ ሥልጣን ለመቆጣጠር ካልተሳካለት ለብቻው ተገንጥሎ ነጻ ሪፑብሊክ ለመመሥረት ዕቅድ ያለው ነው።» (ገጽ 20)
«ሪፈረንደም በሚል ስም የተካሄደው የይስሙላ ሂደት ትግራይ ከኢትዮጵያ መገንጠል ለሚችል የረጅም ጊዜ ዕቅድ መንገድ የሚያመቻችና የሚጠርግ እንጂ፣ የኤርትራን ሕዝብ መብትና ጥቅም ለማስከበር ተብሎ በቅንነት የተቀናጀና የተደራጀ አልነበረም።» (ገጽ 27)
ተስፋጽዮን እንደጠቆሙት የትግሬ-ወያኔዎች «ሥልጣን ላይ ከሌሉ የራስን ዕድል በራስ መወሰን እስከ መገንጠል የሚፈቅደውን ሕገ መንግሥታቸውን ተጠቅመው ትግራይ ከኢትዮጵያ በኃይል ለመገንጠል ሊሞክሩ ነው። ይህንን ዕውን ለማድረግ ደግሞ አስቀድመው የቀረችውን ኢትዮጵያ በረቀቀ መንገድ መበታተን፣ አለያም የሕዝቧን እና የግዛቷን አንድነት የሚያዳክምና የሚያላላ ተግባር ከመፈጸም ወደኋላ አይሉም።» በማለት የትግራይ ሪፑብሊክን የመመሥረቱ ሁኔታ በከፍተኛ ሚስጢር ተይዞ እየተሠራበት መሆኑን ሰሚ ካለ ነግረውናል።
የትግሬ-ወያኔዎች ቀደም ብለው ከ፲፱፻፹፫ ዓም ጀምሮ፣ ከሰሜን ጎንደር እና ሰሜን ወሎ አውራጃዎች የዐማራ ተወላጆችን ገድለው፣ አፈናቅለው እና ማንነታቸውን በግድ አስቀይረው ሠፊ የትግራይ ግዛት መስርተዋል። ሠሞኑን ደግሞ ከተለያዩ የብዙሃን መገናኛ ተቋሞች የተሠራጩ ይፋ መግለጫዎች እንደሚያመለክቱት የትግራይ ግዛት እስከ አል-ውሃ (ወሎ) የሚዘልቅ እንደሆነ ተገልጿል። ወደፊት ደግሞ አሰብን ያካተተ ግዛት ያለው የትግራይ-ትግሪኝ ሪፑብሊክ ለመመሥረት በሠከነ ሁኔታ እየሠሩ መሆኑ ልብ ሊባል ይገባል። የትግሬ-ወያኔ አገር ለማፍረስ ይህን ያህል ርቀት ሲጓዝ፣ «ኢትዮጵያዊ ነኝ» የሚለው ኃይል ግን ይህንን እንቅስቃሴ የሚገታ አንዳችም ተጨባጭ ሥራ ካለመሠራቱም በላይ፤ የአገሪቱን የአፈራረስ ሂደት በቅጡ የተረዳም ሆነ ሊረዳ የሚሻ ወገን ያለ አይመስልም። እነዚህ ሁሉ በአንድነት ተጠቃለው ሲመዘኑ ኢትዮጵያ እንደ አገር መኖሯን የሚያመለክቱ አይደሉም። ዕውነታው አገሪቱ በ፳፬(ሃያ አራት) ዓመታት አዝጋሚ የመፈራረስ ሂደት፣ በሰመመን መልክ እየተበታተነች መሆኑን ነው። ይህ ደግሞ በዕቅድ እና በሰከነ መልኩ በኢትዮጵያ ጠላቶች የተቀነባበረ ረጅም ጊዜ የወሰደ ሂደትን የተከተለ መሆኑን ለአፍታም መዘንጋት የለበትም።

ኢትዮጵያን እና ኢትዮጵያዊነትን የሚወዱና የሚያፈቅሩ ዕውነተኛ ዜጎች፣ «ምኗን ሰዳ ምኗን ጨበጠች» እንዳይሆን ነገሩ፣ ከአሁኑ ተቻችሎ እና ልብ ለልብ ተዋውጦ ይህ ዘረኛ ቡድን የፈለውን ሣያደርግ፣ ኢትዮጵያን የምንታደግበትን መንገድ በጋራ መላ እንድንል ሞረሽ ወገኔ የዐማራ ድርጅት የተለመደ ጥሪውን ያቀርባል። ከሁሉም በላይ የጥፋት ዘመቻ የተከፈተበት የዐማራው ነገድ ተወላጆች ለዚህ ጥሪ የሚያቀርቡት አሉታዊ ምክንያት ሊኖር አይገባም። ጥሪው የሞት፣ የሽረት ነውና ኅልውናችን በማስጠበቅ የኢትዮጵያን ትንሣዔ ዕውን የማድረግ ትውልዳዊ ኃላፊነታችን ልንወጣ ይገባል።

ዐማራውን ከፈጽሞ ጥፋት እንታደግ!

ፈለገ አሥራት የትውልዳችን ቃል ኪዳን ነው!

ኢትዮጵያ በጀግና እና ቆራጥ ልጆቿ መስዋዕትነት አንድነቷ እና ነፃነቷ ተከብሮ ለዘለዓለም ትኖራለች!

The post ምን እየጠበቅን ነው? «የትግራይ ሪፑብሊክ ድንበር አል-ወሃ ድረስ ነው» – ሞረሽ ወገኔ የዐማራ ድርጅት appeared first on Zehabesha Amharic.

ፍርድ ቤቱ የተቃዋሚ ፓርቲ አመራሮች አቤቱታ ላይ ቀጠሮ ሰጠ

$
0
0

በነገረ ኢትዮጵያ ሪፖርተር

10403649_666636843461977_4586775875862445773_nየልደታ ከፍተኛ ፍርድ ቤት 19ኛ ወንጀል ችሎት በዘላለም ወርቃገኘው ክስ መዝገብ የተከሰሱት የተቃዋሚ ፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች በማረሚያ ቤት አስተዳደር ላይ ያቀረቡት አቤቱታ ላይ ውሳኔ ለመስጠት ለየካቲት 25/2007 ዓ.ም ቀጠሮ ሰጠ፡፡ በዛሬው ችሎት የተከሳሾቹ ጠበቃ ተማም አባቡልጉ ‹‹ህዳር 12 ለ 13/2007 ዓ.ም አጥቢያ ድንገተኛ ፍተሻ ተደርጎ የተጠርጣሪዎቹ ንብረት ተወስዶባቸዋል፣ የሰብአዊ ጥሰት ተፈጽሞባቸዋል፣ ድንገተኛ ፍተሻው ህገ ወጥ ነው›› በሚል በቂሊንጦ ማረሚያ ቤት አስተዳደር ላይ ላቀረቡት አቤቱታዎች ማረሚያ ቤቱ የሰጠውን መልስ ሰምቷል፡፡

የማረሚያ ቤቱ መልስ በጽሁፍ ከቀረበ በኋላ በቃልም እንዲቀርብ በታዘዘው መሰረት የቂሊንጦ ማረሚያ ቤት የቀጠሮ ማረፊያ አስተዳደር አስተዳዳሪ ዋና ሱፐር ኢንተንደንት አምባዬ ክቡር ፍተሻው መካሄዱን አምነው ነገር ግን፤ ‹‹ፍተሻው የተከናወነው በፍርድ ቤት ትዕዛዝ ከጠዋቱ 12 ሰዓት በኋላ ነው፡፡ ፍተሸውም በአቤቱታው ላይ እንደቀረበው ባልታወቁ ሰዎች ሳይሆን በቂሊንጦ ማረሚያ ቤት ጥበቃዎች ነው የተከናወነው›› ሲሉ መልስ ሰጥተዋል፡፡ የፍተሻውን አላማም ‹‹የታራሚዎችን ደህንነት ለመጠበቅ ሲባል የተከለከሉ ነገሮችን ፈትሾ ለማስወገድ ነው፡፡ በፍተሸውም ሚስማር፣ ስለት ነገሮች፣ እንዲሁም ብጥብጥ የሚቀሰቅሱ ጽሁፎች ተገኝተዋል፡፡›› ብለዋል፡፡

ባለፈው የአብዛኛዎቹ ተከሳሾች የክስ መቃወሚያ ውድቅ ሲደረግ የ7ኛ ተከሳሽ አብርሃም ሰለሞን፣ እንዲሁም 8ኛ ተከሳሽ ሰለሞን ግርማ የተወሰኑ የክስ ማሻሻያዎች እንዲያደርግ ትዕዛዝ ሰጥቶ እንደነበር ይታወቃል፡፡ በዚህ መሰረት በዛሬው ዕለት በሁለቱ ተከሳሾች ላይ አሻሽየዋለሁ ያለውን ክስ አቃቤ ህግ ይዞ ቀርቦ በንባብ አሰምቷል፡፡

በመጨረሻም በፍተሻው ወቅት ተፈጽሟል በሚል በተከሳሾቹ ጠበቃ የቀረበውን አቤቱታና ማረሚያ ቤቱ የሰጠውን መልስ አገናዝቦ ውሳኔ ለመስጠት እንዲሁም፤ በሁለቱ ተከሳሾች ላይ የቀረበው ማሻሻያ ፍርድ ቤቱ በሰጠው ትዕዛዝ መሰረት ‹‹ተሸሽለዋል ወይንም አልተሸሻሉም›› የሚለውን ለመወሰን ለየካቲት 25/2007 ዓ.ም ጠዋት 3 ሰዓት ላይ ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡

The post ፍርድ ቤቱ የተቃዋሚ ፓርቲ አመራሮች አቤቱታ ላይ ቀጠሮ ሰጠ appeared first on Zehabesha Amharic.

በጆርጂያ አትላንታና አካባቢው ለምትኖሩ ኢትዮጵያውያን –የአድዋ ድል በዓል ጥሪ

የአድዋ ድል በዓል ጥሪ –በሚኒሶታና አካባቢው ለምትኖሩ ኢትዮጵያውያን እና ኢትዮጵያን ወዳጆች

$
0
0

የኢትዮጵያ ኮምዩኒቲ በሚኒሶታ የአድዋ ድል በዓልን በማስመልከት ልዩ የሆነ ትምህርታዊ ዝግጅት አሰናድቷል:: በመሆኑም በሚኒሶታ እና አካባቢው የምትገኙ ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ ኢትዮጵያውያን በዝግጅቱ ላይ እንድትታደሙ ተጋብዛችኋል:: ፍላየሩን ይመልከቱ::
adwa Minnesota

The post የአድዋ ድል በዓል ጥሪ – በሚኒሶታና አካባቢው ለምትኖሩ ኢትዮጵያውያን እና ኢትዮጵያን ወዳጆች appeared first on Zehabesha Amharic.

Health: በትዳሬ ውስጥ ምንም ዓይነት ፀብና ግጭት አለመኖሩ ችግር ይኖረው ይሆን?

$
0
0

Young couple in bed, looking away from each other
አንዳንድ ጊዜ በትዳሬ ውስጥ አንድ የሆነ የጎደለ ነገር ይኖር ይሆን ስል አስባለሁ፡፡ ምክንያቱም እኔና ባለቤቴ ፈፅሞ ተጣልተን (ተደባድበን) አናውቅም፡፡ አይደለም መደባደብ ተጨቃጭቀን እንኳን አናውቅም፡፡ በእርግጥ ሁለታችንም የመጣነው እጅግ በጣም ወግ አጥባቂና ሃይማኖተኛ ከሚባሉ ቤተሰቦች ሲሆን ሁለታችንም አባትና እናቶቻችን ሲጨቃጨቁም ሆነ ሲደባደቡ አላየንም፡፡ በብዙ ነገር ተስማምተን እንኖራለን፡፡
በእርግጥ እውነት ለመናገር ትዳራችንና የፍቅር ግንኙነታችን በጣም ፍቅር የተሞላበት የሚባል አይደለም፡፡ ከዚህ ይልቅ ፀጥ ያለ…. የተረጋጋና ጥንቃቄ የተሞላበት ነው ቢባል ይበልጥ ይገልፀዋል፡፡ ለመሆኑ ውድ አማካሪ የሆነ ያጣነው ነገር ያለ አይመስልህም?
ሰፈር/
ዮዲት ነኝ ከ/ወሎ

ውድ ዮዲት፡- ግምትሽ ትክክል ነው፡፡ አ ዎ ን በትክክል ይኖራል፡፡ አንቺና ባለቤትሽ የፈለገውን ያክል የተጣጣማችሁና ፍፁም አብራችሁ የምትሄዱ ብትሆኑም እንኳን ሁለት የተለያያችሁ ሰዎች መሆናችሁን መዘንጋት የለባችሁም፡፡ ምናልባት ነገረኛ ላለመባል እየፈራችሁ ካልሆነ በቀር በየቀኑ አንድ ቤት ውስጥ እየኖራችሁ አንድም ቀን ተጣልተን አናውቅም ማለት የማይመስል ነገር ነው፡፡

እኔ በበኩሌ ፈፅሞ አንጋጭም የሚሉ ጥንዶች ‹ጥንቃቄ የተሞላበት የፍቅር ግንኙነት›› (Careful loving) ውስጥ ናቸው ነው የምለው፡፡ ከሁለት አንዳቸው ወይም ደግሞ ሁለቱም ማንኛውም አይነት ግጭት ወይም ፀብ የፍቅር ግኑኝነታችንን ይጎዳል ብለው ይሰጋሉ ፡ ፡ በዚህ የተነሳ በሚችሉት አቅም ሁሉ ፀብን ሲሸሹ ይኖራሉ፡፡ የዚህ ውጤቱ ታዲያ ህይወት ህይወት የማይሸት ደባሪ (አሰልቺ) የሆነ ትዳር ይሆናል፡፡

አንቺም እራስሽ የትዳር ህይወታችሁ ያን ያክል ፍቅር የተሞላበት ነው የሚባል አይነት እንዳልሆነ ነው የገለፅሽው፡፡ ነገር ግን ማወቅ ያለብሽ ነገር ንዴት፣ ቁጣ ሃዘን፣ ብስጭት….. ወዘተ ያሉትን አሉታዊ ስሜቶች በመውስጣችን አምቀን ስንይዛቸው ፍቅርና ርህራሄ እንዲርቁን እናደርጋለን፡፡ አንቺና ባለቤትሽም እነዚህን የፍቅርና ርህራሄ ስሜቶቻችሁን በደግነታችሁ እየገደላችኋቸው ነው፡፡

እንደ ገለፅሽው አንቺም ሆንሽ ባለቤትሽ የመጣችሁበት ቤተሰብ በአሁኑ ስብዕናችሁ ትልቅ ተፅዕኖ አሳድሮባችኋል፡፡ ብዙ ጊዜ እንደሚታወቀው ቁጥጥር ከሚያበዙ ወይም ወግ አጥባቂና በጣም ሃይማኖተኛ ቤተሰብ የሚወጡ ልጆች እንደ እንዴት ቁጣ …. ወዘተ ያሉ አሉታዊ ወይም ቅዱስ ያልሆኑ ስሜቶች ሃጢያት እንደሆኑ እየተነገራቸው ነው የሚያድጉት፡፡ ፍርሃትም እንደዚያው ሃጢያት ነው ይባላል፡ ፡ የእምነት ማጣት ምክልት ነውም ይባላል፡፡ በዚህ የተነሳ ባለቤትሽ የሚያናድድሽን ነገር እንኳን ቢያደርግ አንቺ የተሰማሽን ስሜት አምቀሽ ትይዥዋለሽ፡፡ ይህ ነገርም በየጊዜው እየተደጋገመ ሲሄድ በመጨረሻ ውጤቱ ታማኝነትና መቀራረብ የራቀው ትዳር ይሆናል፡፡

በእርግጥም መልካሙ ነገር አንቺም ሆንሽ ባለቤትሽ ችግሩን ተረድታችሁ ለውጥ ለማምጣት ፍላጎት አላችሁ፡፡ ለዚህ ደግሞ ሁሉንም ስሜቶቻችሁን በግልፅነት ለመጋራትና ትዳራችሁን መልሳችሁ እንደ አዲስ ለመገንባት ለራሳችሁ ቃል ግቡ፡፡ ጤናማና ደስታ የተሞላበት ትዳር ለመገንባት የሚረዱ ፅሁፎችን አንብቡ፡፡ የተለያዩ ትምህርታዊ ገለፃዎችን ተከታተሉ፡፡ ከ ሁሉም በላይ ግን ትዳራችሁን በየዕለቱ የሚከሰቱ ግጭቶችንና አለመግባባቶችን መቋቋም ብቻ አይደለም፡፡ ይልቁንስ እያንዳንዷ ግጭት አልፋችሁ ወደ ፍቅራችሁ በተመለሳችሁ ቁጥር ፍቅራችሁ የበለጠ እያደገ እየጠነከረ እንደሚሄድ ሙሉ እምነት ይኑራችሁ፡፡

ይህ ጽሁፍ በቁምነገር መጽሄት ላይ ታትሞ ወጥቷል::

The post Health: በትዳሬ ውስጥ ምንም ዓይነት ፀብና ግጭት አለመኖሩ ችግር ይኖረው ይሆን? appeared first on Zehabesha Amharic.


አቶ አሰፋ ጫቦን ለቀቅ… ከሺመልስ አበበ

$
0
0
አቶ አሰፋ ጫቦ

አቶ አሰፋ ጫቦ

አቶ አሰፋ ጫቦ በኢሳት ቴሌቪዥን፣ በአዉራምባ ታይምስ ድህረ ገጽና በፊንፊኔ የድህረ ገጽ ሬድዮ ያደረጉትን ቃለ መጠይቆች ተመልክቻለሁ፤ አድምጫለሁ። እንዲሁም በኢትዮሚዲያ ድህረ ገጽ ላይ በብእር ስሙ መላኩ ይስማዉ የሚባል ግለሰብ የጻፈዉን ዉርጅብኝ አንብቤ በጣም ከልቤ አዘንኩ። በፍኖት ሬድዮም ስለ አቶ አሰፋ የተለፈፈዉን ተራ ትችትና ዘለፋም ሰምቼ በጣም አዘንኩ። አቶ አሰፋ የተናገሩትን በመረጃም ሆነ በሙግት መልክ በሰለጠነ መንገድ አንድ በአንድ መሻር ሲቻል ከደረጃ ዝቅ ባለ መንገድ ተራ ትችት ዉስጥ መግባቱ ከግምት ያስገባል እንጂ ሌላ እዉቀት የሚጨምር አይደለም። ለመሆኑ መቼ ነዉ የሰለጠነ ዉይይት የሚደረገዉ?

ይህ አይነቱ ስም የመጥራትና አወቅሁሽ ናቁሽ ትችት በቀድሞዉ ቀዝቃዛ ጦርነት ጊዜ ሲካሄድ የነበረ ባህርይ በአሁኑ ወቅት እተካሄደ ማየቱ ምን ያህል ሗላቀር የፖለቲካ ባህርይ እንደሆነ መረዳት አያዳግትም። በደርግ ጊዜ የነበረን የፖለቲካ ቆርሾ በአሁኑ ሰአት እንዳለ መድገም ደግሞ መለወጥ አለመቻልን የሚያመለክት ይመስለኛል። በአቶ አሰፋ ላይ የተካሄደዉ አግባብ የሌለዉ ትችት ይህንን መልስ እንድሰጥ አስገድዶኛል።

እኔ አቶ አሰፋ ጫቦን አዉቃቸዋለሁ። በመጀመሪያ ያወቅሗቸዉ የጋርዱላ አዉራጃ አስተዳዳሪ ሆነዉ ጊዶሌ ከተማ ሲመጡ ነዉ።
በየካቲት ስድሳ ስድስት አመተ ምህረት ንቅናቄ አርባ ምንጭ መጥተዉ ከሼቻ (የላይኛዉ ከተማ) ወደ ሲቀላ (የታችኛዉ ከተማ) ይነዱ በነበሩት ጉርድ ላንድሮቨር ከሌሎች ተማሪዎች ጋር ሆኜ ወስደዉናል። በፈገግታ ላንድሮቨሩን አቁመዉ ግቡ ብለዉን ስለለዉጡ እያወሩንና እኛም ደግሞ በአንክሮ እያዳመጥን እንደነበር አስታዉሳለሁ። ደርግ ስልጣን ላይ ወጥቶ እድገት በህብረትን አዉጆ እኔም ደግሞ ከአርባ ምንጭ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ወደ ከምባ ወረዳ ከአዲስ አበባ ከመጡ ዘማቾች ጋር ዘመትኩ። ታናሽ ወንድማቸዉ የሆነዉ እሸቱ ጫቦም እንዲሁ ዘምቶ ነበር።

ዘመቻዉን ጥዬ ስመለስ አቶ አሰፋ የህዝብ ድርጅት ጉዳይ ጊዚያዊ ጽህፈት ቤት ዋና ጸሀፊ ሆነዉ እንደተሾሙ አርባ ምንጭ ከተማ ሰማሁ። ይህ መስሪያ ቤት ካድሬዎችን ቀጥሮ በየቦታዉ እየላከ ቅስቀሳ የሚያስደርግ መስሪያ ቤት እንደሆነም በወቅቱ ተረዳሁ። በወቅቱ በነበረኝ ንቃተ ህሊናና ከጓደኖቸም ካገኘሁት ምክር ከአቶ አሰፋ መራቁ የተሻለ ነዉ የሚል እምነት አሳድሮብኝ ነበር።እ. ኢ. አ. በ1969 ዓ. ም. ትምህርት ጀመርን። በኢሕአፓ እና በመኢሶን መካከል ይካረር ነበረዉ የፖለቲካ ትግል በአርባ ምንጭ ከተማና በነበርኩትም ትምህርት ቤትም ይብላላ ነበር።

እ. ኢ. አ. በ1969 ዓ. ም. በአንድ ወቅት የአርባ ምንጭ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት መማሪያ ክፍሎች ዴስኮች ላይ ለእያንዳንዱ ተማሪ ተብሎ በእጅ የተጻፉ የኢሕአፓ ወረቀቶች ተበትነዉ ነበር። ክፍል ስገባ ወረቀቱን አነበብኩ። ወረቀቱ የተሞላዉ በኢህአፓ መፈክሮች ነዉ። እያንዳንዱም ተማሪ አንብቦት ዝም ብሏል። ትምህርትም ተጀምሮ ሳለ የአርባ ምንጭ ወረዳ ፖሊስ ጣቢአ አዛዥ የነበረ ሻምበል ተስፋዬ የሚባል ከጠቋሚ ተማሪዎች ጋር በመሆን በየክፍሉ እየዞረ ማን ነዉ ወረቀት የበተነዉ እያለ ይጮህ ነበር።እኔ የነበርኩበት ክፍልም መጥቶ ጮኸብን። ብዙ ተማሪዎች ክፍል ለቅቀዉ ሲወጡ እኛም ወጣን። ብዙ ጠቋሚ ተማሪዎች በቦክስ ተመቱ። ቁጥሩ አንድ መቶ የሚሆን ማስ የሚባል (ፈረንሳይ የተሰራ አስር ጥይት ጎራሽ) ግማሽ አዉቶማቲክ ጠብመንጃ የታጠቀ የፈጥኖ ደራሽ ሀይል ትምህርት ቤቱን ከበበ። በዚህን ጊዜ ነበር አቶ አሰፋ ጫቦ ወደ ትምህርት ቤታችን የመጡት።

አቶ አሰፋ በጉርድ ላንድሮቨር ሲመጡ ተማሪዎች አሰገቧቸዉ ብለዉ ሲጮሁ ዋና መግቢያዉን በር ይጠብቁ የነበሩት ተማሪዎች አስገቧቸዉ። ከዚያም ሰንደቅ አላማ የሚከበርበት ቦታ መኪናዉን አቁመዉ ከመኪና ሲወጡ ተማሪዎች ከበቧቸዉ። ከዚያም ተማሪዎች ጪኸታቸዉን ማሰማት ጀመሩ። አቶ አሰፋ የላንድሮቨሩ ሞተር ኮፈን ላይ ቆመዉ ሳለ የድምጽ ማጉያ ተሰጥቶአቸዉ ከተማሪዎች ጥያቄ መቀበል ጀመሩ። ከዚያም መልስ መስጠት ጀመሩ። ተማሪዎች በጥሞና አዳመጧቸዉ። እርሳቸዉም “…ይህቺ የዴሞ ቅስቀሳ ነች። ትምህርታችሁን ብትከታተሉ ይበልጥ ትጠቀማላችሁ…” ብለዉ ተናገሩ። ሌሎች መልሶችም ባያረኩን እንኳ እሳቸዉ ምልስ ሊሰጡ እንደማይችሉ ተማሪዎች የተረዱትም ይመስለኛል። በቦክስ የተመቱና የደሙ ተማሪዎች በአምቡላንስ ወደ ሆሲፒታል ተላኩ። ጥቃቱን የፈጸሙ ተማሪዎች ከተጠያቂነት እንደማይድኑ አቶ አሰፋ ማሳሰቢያ ሰጡ። ይህ እየሆነ ሳለ የመቶ አለቃ ጳዉሎስ ቦጋለ መጥቶ አቶ አሰፋ እንዲናገር እድል ሲሰጠዉ ድምጽ ማጉያዉን ተቀበሎ መደንፋት ጀመረ። “…የአድሀሪያን ልጆች የሬሳ ሳጥን በሚያክል አገልግል ፍትፍትና ጭኮ እየተላከላቸዉ ተንደላቅቀዉ እየተማሩ የጭቁን ልጆች እንዳይማሩ ለማድረግ የተጠነሰሰ ሴራ ነዉ…” እያለ ደነፋ። ብዙ ዛቻዎችንም ዛተ። ከዚያም አቶ አሰፋ ከመቶ አለቃ ጳዉሎስ ጋር ለጥቂት ደቂቃዎች ተነጋገረ። የመቶ አለቃ ጳዉሎስ እየተቆጨ ሲናገር እንደነበር ታዘብኩ። ኮሎኔል ተስፋዬ የሚባል የፈጥኖ ደራሽ ሀይሉን መርቶ የመጣዉ ወደነርሱ ጠጋ ብሎ የነገሩትን ሰምቶ ሄደ። ከዚያም አቶ አሰፋ ለዚያኑ ቀን ትምህርት እንደሌለና ወደ ቤታችን እንድንሄድ ነገሩን። እኛም ወደ ቤት ስንሄድ የታዘብኩት ነገር ቢኖር የመቶ አለቃ ጳዉሎስ ቦጋለ ከአቶ አሰፋ ጋር ሲጨቃጨቅ እንደነበር ነዉ። በወቅቱ ከጓደኞቼ ጋር ስንነጋገር የደረስንበት መደምደሚያ ቢኖር የመቶ አለቃ ጳዉሎስ እርምጃ ለመዉሰድ ፈልጎ በአቶ አሰፋ እምቢተኝነትና ተጽእኖ ደም ላይፈስ እንዳልቻለ ነዉ። በወቅቱ ቁጥሩ አንድ መቶ የሚሆነዉ የፈጥኖ ደራሽ ሀይል የግድያ ትእዛዝ ቢሰጠዉ ኖሮ ምን ያህል ተማሪ እንደሚሞት መገመት አያዳግትም.። በተማሪዎችም ዘንድ አቶ አሰፋ ክብር ሊያገኙም ችለዋል ይህችን ዉለታ ለተማሪዎች ስለዋሉ።

ከአቶ አሰፋ ጋር በርእዮተ አለም አመለካከት ብለያይም አንኳ በእርሳቸዉ ብርታት ከሞት ልድን ችያለሁ። በወቅቱ ከከበቡን ፈጥኖ ደራሾች ቢያንስ ወደ አስር የሚሆኑትን አዉቃቸዋለሁ። ተማሪዎች የነበሩ ናቸዉ። በሌላ ወቅት አግኝቼ ስጠይቃቸዉ በአቶ አሰፋ እምቢተኝነት የመቶ አለቃ ጳዉሎስ ቦጋለ ትእዛዝ ለመስጠት እንዳልፈለገ አዛዣቸዉ የነበረዉ ኮሎኔል ተስፋዬ እንደነገራቸዉ አጫወቱኝ። ትእዛዝ ቢሰጣቸዉ ኖሮ እኔንም ሊገድሉ እንደሚችሉ ነገሩኝ። እኔም የህችን የአቶ አሰፋን ዉለታ ሁል ጊዜ እንዳስታዉስ አደረገኝ። አቶ አሰፋን ወድጄ አላዉቅም። ግን ይህ ዉለታቸዉ እንዳከብራቸዉ አድሮጎኛል።

ብዙ ሰዎችን አስገድለዋል የሚል ክስና ስሞታ በተደረጉት ትችቶች ዉስጥ ተካትተዋል። አርባ ምንጭ ዉስጥ የተደረጉት ግርፊያዎች ናቸዉ የኢሕአፓን አባላትና ደጋፊዎች ለማጋለጥ ተብሎ። ፋሺስቱ አሊ ሙሳ በገዛ እጁ የገደላቸዉ አተ ተፈሪ (የእኔ ዘመድ የሆነችዉ አየለች ማመጫ ባለቤት)፣ ክፈተዉ (የአጎቴ ባለቤት ወንድም)፣ እና ኑሩ (አቶ አሰፋ ሲታሰሩ በእርሳቸዉ ምትክ የተመደበዉ) ሲሆኑ አርባ ምንጭ ዉስጥ ምንም የፖለቲካ ግድያ አልተካሄደም። አንድም የኢሕአፓ አባል አልተገደለም። ግርፋት ግን ተካሂዷል። በጎፋ አዉራጃ ዋና ከተማ ሳዉላ ከተማ የመቶ አለቃ ጳዉሎስ ቦጋለ ፊዉዳሎች ናቸዉ ብሎ የረሸናቸዉ ጥቂት ግለሰቦች ናቸዉ። የገለብና ሀመር ባኮ አዉራጃ ዋና ከተማ ዉስጥ አንድ የጊዶሌ ተወላጅ የሆነ ካድሬ አንድ ነጋዴ ገድሏል። እ. ኢ. አ. በነሐሴ ወር 1976 ዓ. ም. (August 1984 G. C.) ለትምህርት ኢትዮጵያን ለቅቄ እስከምወጣ ድረስ እዚያዉ ጋሞ ጎፋ የኖርኩ ስለሆነ ሁኔታዎችን ጠንቅቄ አዉቃለሁ። በአቶ አሰፋ ላይ የተደረገዉ አሳዛኝ ትችት ከእዉነት የራቀ መሆኑ በጣም አሳዘነኝ። ጸሀፊዎቹና ተቺዎቹ ከተባራሪ ወሬ የቀሰሙትን ነገር እንደ እዉነታ አድርገዉ ማቅረባቸዉ ዋጋ ቢስነቱን ከማጋለጥ በስተቀር የሚያመጣዉ ነገር ያለ አይመስለኝም። አቶ አሰፋ ቢጠየቁም እንኳ በኢሕአፓነት ተጠርጥረዉና ታስረዉ ለተገረፉት እንጂ በአስገዳይነት አይደለም። ብዙ ተማሪዎች በኢሕአፓነት ተጠርጥረዉ በተለያዩ ቦታዎች ታስረዉና ተገርፈዉ ወደ ሰላማዊ ኑሮና ትምህርት እንዲመለሱ ተደርጓል። ግድያ እንዳይካሄድ ካድሬዎች እንኳ አቶ አሰፋን ያሙ የነበረ ለመሆኑ ሲነገር ሰምቻለሁ። አቶ አሰፋ ኢሕአፓዎች እንዳይገደሉ አድርገዋል። ጋሞ ጎፋ ዉስጥ ባጠቃላይ እስራትና ግርፊያ ተካሄደ እንጂ የፖለቲካ ግድያ አልተካሄደም። ይህ ደግሞ በአዲሰ አበባና ሌሎች ከተሞች አንዳንድ የቀበሌ ሊቀመናብርት በቀይ ሽብር ወቅት ወጣቶች እንዳይገደሉባቸዉ ያስሯቸዉና ይገርፏቸዉ ከነበረዉ በምንም ተአምር አይለይም።

ኢሕአፓዎች ያደረጉትስ የከተማ ቃፊር የግድያ ዘመቻ እና በመካከላቸዉ በነበረዉ የፖለቲካ መከፋፈል እርስ በእርስ የተጋደሉት፤ እንዲሁም ወጣቱን ያስጨረሱት ተረሳና የአቶ አሰፋ ድርጊት ጎልቶ ታይቶ ነዉ ወይ እንዲህ አይነቱ ትችት የተደረገዉ? ትችት በትክክል መረጃ ተይዞ ሲቀርብ ያምራል። ያለበለዚያ ቂም መወጣጫ ወይም ለፖለቲካ ፍጆታ ይዉላል። ደርግም፣ ኢሕአፓም፣ መኢሶንም፣ ወያኔም ሆን ማንም ድርጅትም ሆነ ግለሰብ ከተጠያቂነት አይድንም።

ኢትዮጵያ ለሁላችንም እኩል እናት አገር ነች። ማንም ከማንም አይበልጥም። የበደሏት፣ የገደሏትና የሞቱላትም እንዲሁ አሉ። እያንዳንዱ ትዉልድ የራሱ የሆነ ባህርይ እንዳለዉ ሁሉ ለቀጣዩ ትዉልድ የሚያስተላልፈዉ ትምህርት ገንቢ ሀሳብና ራእይ ያለዉ ቢሆን ይመረጣል። ካልሆነም ደግሞ የታሪክ ተወቃሽ ሆኖ ይቀራል። አገር በቂም በቀል የሚመራ መሆን የለበትም። ታሪክም ቢሆን የሚጻፈዉ በቂም በቀል አይደለም። ወቀሳ፣ ትችትና ሂስ ገንቢ የሚሆኑት አግባብ ባለዉ ሁኔታ ሲፈጸሙ ነዉ። ታሪክም እንዳይወቅሰን ደግሞ ብናስብበት የበለጠ ጠቃሚነት አለዉ ብዬ አምናለሁ።

ሺመልስ አበበ
shimelisabebe@gmail.com

The post አቶ አሰፋ ጫቦን ለቀቅ… ከሺመልስ አበበ appeared first on Zehabesha Amharic.

በርዕሰ አድባራት ለንደን ደብረ ጽዮን ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን ዙሪያ አዳዲስ መረጃዎች

$
0
0

ለርዕሰ አድባራት ለንደን ደብረ ጽዮን ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን አባላት፤ እንዲሁም በUK እና በመላው ዓለም ለምትገኙ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተወሕዶ ሃይማኖት ተከታዮች በሙሉ።
በመጀመሪያ በቸሩ ፈጣሪአችን ሥም የከበረ ሰላምታችን ይድረሳችሁ።

london Church

በስደት ሀገር ከተመሠረተች 40 ዓመታትን ያስቆጠረቸው ርዕሰ አድባራት ለንደን ደብረ ጽዮን ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን ለአያሌ ዓመታት የምእመኗ ሰላምና አንድነት ተጠብቆ በመቆየት ለከፍተኛ የዕድገት ደረጃ ከደረሰች በኋላ እነሆ ባለፉት ሁለት ዓመታት ግን ሰላሟ ተናግቶ የቤተ ክርስቲያኗ በጎ ገጽታና መልካም ምሳሌነቷ ይልቅ በስሟ የሚፈጸመው ክፉውና አሳዛኙ ተግባር ጎልቶ እየተስተጋባ ብዙ ክርስቲያኖችን ሲያሳዝንና ግራ ሲያጋባ ቆይቷል።

Click Full Story in PDF

The post በርዕሰ አድባራት ለንደን ደብረ ጽዮን ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን ዙሪያ አዳዲስ መረጃዎች appeared first on Zehabesha Amharic.

የሕወሓት አስተዳደር ሙስሊሞችን ከየአካባቢው እያደነ ማሰሩን ቀጥሏል

$
0
0

ጋዜጠኛ የሱፍ ጌታቸው በፌስቡክ ገጹ እንዳስታወቀው በርካታ ንፁሃን ወንድሞቻችን ከመዲናችን አዲስ አበባ እየታደኑ ነው።

(ፎቶ ከፋይል)

(ፎቶ ከፋይል)


“ህወሃት መራሹ ወያኔ አሁንም ንፁሃን ሙስሊሞችን ከየአካባቢው ማደነኑን ቀጥሏል።” ሲል ዘገባውን የጀመረው ጋዜጠኛው በዛሬው እለት በብርጭቆ አካባቢ ኮንዶሚኒየም ይኖር የነበረው ወንድማችን የሆነው እና የቢላል ሬዲዬ ጋዜጠኛ የነበረው ፣ ከአመት በፊት በረመዳን ወር መግቢያ ላይ በ3ተኛ ፖሊስ ጣቢያ ታስሮ የነበረው ጋዜጠኛ ካሊድ ሙሃመድ በዛሬው እለት የፈጅር ሰላቱን ሰግዶ ወደ ቤቱ በሚመለስበት ወቅት በደህንነት ሀይሎች ታፍኖ እየተደበደበ ወዳልታወቀ ቦታ ተወስዷል ብሏል::

እንደ ጋዜጠኛው ዘገባ ካሊድ መሃመድ ከቤቱ ውስጥም ላፕቶፖችን ጨምሮ በርካታ የሚገለገልባቸውን ንብረቶች ተወስዶበታል:: ካሊድ በአሁኑ ወቅት የ2 ወር ልጅ ያለው ሲሆን በዛሬው እለት የደህነነት ሃይሎች በአራስ ባለቤቱ ላይም ከፍተኛ ድብደባ እንደፈፀሙ ለማወቅ ተችሏል።

The post የሕወሓት አስተዳደር ሙስሊሞችን ከየአካባቢው እያደነ ማሰሩን ቀጥሏል appeared first on Zehabesha Amharic.

መዓት አውርድ! –አስራት አብርሃም

$
0
0
Asrat Abrha

አስራት አብርሃም

በዘመነ አፄ ልብነድንግል ጦርነት በመጥፋቱ ንጉሱ ጦርነት አውርድ ተብሎ በየቤተክርስቲያኑ ፀሎት እንዲደረግ ትዕዛዝ አውርዶ ነበር እየተባለ በአፈ ታሪከ ይነገርለታል፤ 24 ዓመት የሞላው የህወሀት/ኢህአዴግ ስርዓትም ጦርነት አውርድ፣ መዓት አውርድ እያለ እንደሚገኝ ከደርጊቶቹ ሁሉ መረዳት የሚቻል ነው። አንድነት ፓርቲ በኃይልና በውንብድና እንዲፈርስ ከተደረገ በኋላ ምንም የማደርገው ነገር ስላነበረ፤ ቤቴ ሄጄ ነው ቁጭ ያልኩት፤ ከፌስቡክም ገለል ለማለት ፈሊጌ ነበር ለጊዜው! እነርሱ ግን መቼ ያስቀምጣሉ፤ መቼ ይተዋሉ፤ ቤትህ ድረስ መጥተው ሰላም ይነሱሃል፤ ዝም ብትል የሆነ ነገር አስቦ ነው ይሉሀል፤ ብትናገር በተናገርከው ቂም ቋጥረው ያጠቁሃል፤ ብትፅፍ በሽብር ይከሱሃል፤ ከሰው ያስሩሃል፤ አስረው አይተውሁም፤ ያሰቃዩሃል፤ ይገርሁፋል፤ ቤተሰብ ዘመድ እንዳይጠይቁህ ያድርጋሉ፤ በምንም መንገድ አይተውሁም፤ ቢገድሉህ እንኳ ስምህን፣ ታሪክህን ያጠፋሉ፤ ምን ዓይነት ስርዓት ነው የገጠመን!

ባለፈው እሁድ ማታ የዱርዬ አለባበስ የለበሱ ሁለት ወጣቶች የተከራየሁበት ቤት በር ድረስ መጥተው እንፈልገሃለን አሉኝ፤ እናንተ ደግሞ እነማናችሁ፤ በዚህ ሰዓት የምትፈልጉኝ አልኩዋቸው በጥንቃቄ ራቅ ብዬ እንደቆምኩ፤ ጊዜ የሰጠው ቅል ድንጋይ ይሰብራል ይባል የለ፤ የትዕግስቱ አወሉ ጎረምሶች ይሆናሉ ብዬ ነው ጥንቃቄ ማድረጌ! ከደህንነት መስሪያቤት ነው የመጣነው ሲሉኝ ለካ የዋናው ጎረምሶች ኖሯል ብዬ እየተደነቅኩ አሁን ከምትሉት መስሪያቤት ለመምጣታችሁ በምን ማወቅ ይቻላል አልኩዋቸው አንደኛው የሆነ መታወቂያ አውጥተው አሳየኝ፤ መሽቶ ስለነበር የመታወቂያውን ይዘት በደንብ ለማየት አልቻልኩም፤ የሆነ ሆኖ “በዚህ ሰዓት እኔን ማናገር አትችሉም፤ መሽተዋል አንድ ሰዓት ሊሆን ነው አልኩዋቸው።”

አንዱ ፈጠን ብሎ መረጃ ፈልገን ነው አለ፤

ለመሆኑ ምን ዓይነት መረጃ ነው የምትፈልጉት ስለው፤

አቶ በላይ ፍቃዱ ከሀገር ስለወጣበት ሁኔታ የምታውቀው ነገር ካለ እንድትነግረን ነው።

በዚያ በበራችሁ መሰለኝ የሄደው አልነበራችሁም እንዴ! በማለት መለስኩለት (እንደ አቡነ ቴክለሃይማኖት ክንፍ አውቶ ሄደ ባልኩዋቸው ኖሮ!)

እየቀለድን እኮ አይደለም፤ አለ አንደኛው።

እኔም እየቀለድኩ አይደለም፤ በመሰረቱ እኔ ስለምትሉት ጉዳይ የማውቀው ነገር የለም፤ አንድነት በኃይል ከተወሰደብን ጀምሮ አግኝቸው አላውቅም፤ እኔ ደግሞ ቤቴ ነው ያለሁት፤ ሰው ሲተው አታውቅም እንዴ! አንዳንዴ እኮ ሁሉም ነገር መዝጋት ጥሩ አይደለም፤ መዓት አውርድ እኮ አይባልም፤ ይህን ሄዳችሁ ለአለቆቻችሁ ንገሩልኝ ብዬ ቀለል አድርጌ ሸኘሁዋቸው፤ ከተላላኪ ጋር አታካራ ውስጥ መግባት ትርጉም የለውም ብዬ ነው።

ጉዳዩ ግን በዚህ ብቻ አላበቃም፤ እንደገና ዛሬ ደግሞ የቀበሌ ካድሬዎች የተከራየሁበት ቤት ድረስ መጥተው የቤቱን ባለቤት የክራይ ውል አለህ ወይ? መታወቂያው ኮፒ አድርገሀዋል ወይ? አዋከቡት፤ የእኔን ስምም መዝግበው ይዘው ሄደዋል። እነዚህ ተላለኪዎች ደግሞ በተራው እኔን ግዳይ ጥለው ለመሾም፣ ለመታመን ይፈልጋሉ፤ እንግዲህ ዋናዎቹ መወሰን አለባቸው፤ እኔ በቦታዬ ነው ያለሁት፤ መግደልም ማሰርም ይችላሉ። ግን ምን ይሆን የሚፈልጉት! ፓርቲ መስርተህ ስትታገል ሊያጠፉህ ይፈልጋሉ፤ ቤትህ አርፈህ ስትቀመጥ ቤትህ ድረስ መጥተው ሰላም ይነሱሃል፤ ይሄ መዓት አውርድ እንጂ ሌላ ስም ልሰጠው አልችልም፤ መዓቱን ያውርድላቸው እንጂ እኔማ ምን ማለት እችላለሁ!

እዚህ ሀገር ግለሰቦች እንደፈለጉ ነው የሚያጠቁህ፤ ከለላ የሚሰጥህ የህግ ይሁን የመንግስት ተቋም ያለ አይመስለኝም፤ ይሄ ነው ደግሞ በጣም አሳዛኙ ነገር! በሌላ በእኩል ደግሞ እነርሱ ለፍትህ፤ ለሰላም እና ለዴሞክራሲ ታገልን ብለው አርባኛ ዓመታቸው እያከበሩ ነው፤ በመሬት ላይ ያለው እውነታ ግን ሌላ ነው። ዛሬ እነርሱ በሚመፃደቁበት ዕለት እነ አብርሃ ደስታ፣ እነ ሀብታሙ አያሌው፣ እነየሽዋስ፣ እነዳንኤል እንዲሁም የዞን ዘጠኝ አባላትና ሌሎችም የህሊና እስረኞች የፍርድ ቤት ቀጠሮ ነበራቸው፤ ፍትህ አጥተው እነርሱና ቤተሰቦቻቸው እየተንከራተቱ ነው ያሉት። እንግዲህ የህወሀት የአርባ ዓመት ጎዞ የሚያሳየው ፍትህ፣ ሰላምና ዴሞክራሲ አይደለም፤ ዘረኝነት ነው የነገሰው፤ ፍትህ አልባነት ነው የሰፈነው፤ የባህር በራችን ነው ያሳጣን! ምንም የሚያኮራ ነገር የለውም!

በመሰረቱ የትግራይ ህዝብ እነርሱ ብቻ አይደለም የወለደው፤ ጦርነት የዋለውም ከእነርሱ ጋር ብቻ አይደለም። የህወሀት ሰማዕታት ብቻ አይደሉም የትግራይ ሰማዕታት፤ የትግራይ ህዝብ በብዙ ጦርነቶች ላይ ውለዋል፤ መተማ ላይ ውለዋል፤ ጉራዕ ላይ ውለዋል፤ ጉንዳጉንዴ ላይ ውለዋል፤ ዶጋሊ ላይ ውለዋል፤ አድዋ ላይ ውለዋል፤ ማጨው ላይ ውለዋል፤ አላጄ ላይ ውለዋል። በእነዚህ ጦርነቶች ሁሉ የተሰዉ ልጆች አሉት፤ ሰማዕታት አሉት። ስለሀገሩ ክብር፣ ስለሃይማኖቱ ብሎ አንገቱን ለጎራዴ የሰጠ ንጉስም ነበረው። የትግራይ ህዝብ ብዙ ብዙ ሰማዕታት ነበሩት! የሀገር አንድነት ያስጠበቁ፤ ባህሩንና የብሱን በብርቱ ክንዳቸው ስር ያኖሩ ጀግኖች ነበሩት። የትግራይ ህዝብ ለጀግኖችም ለሰማዕታትም አዲስ አይደለም!

The post መዓት አውርድ! – አስራት አብርሃም appeared first on Zehabesha Amharic.

ዕቢያ አፈር ልሶ ተነሳ –ከአበበ ከበደ

$
0
0

ደርግ ወገቡን እየደበደበ ያቆሳሰለው በመጨረሻም በጾረናና ዛላንበሳ ጦር ሜዳ ላይ ራሱን ክፉኛ የተቀጠቀጠው እባብ አፈር ልሶ ተነሳ። እባብ ራሱን ተቀጥቅጦ ሞቶ እንኳን ቢሆን ሊነሳ ይችላልና መፍትሄው የዛፍ ቅርንቻፍ ላይ ወይም ገመድ ላይ ሰቅሎ መተው እንደሆነ ይታወቃል። ይህ እላይ የተሰቀለ እባብ ድንገት ቢነቃ እንኳን መላወስ ስለሚያቅተው እዚያው ሞቶ ደርቆ ይቀራል። እባብን ሞቷል ብሎ ሜዳ ላይ፣ ያውም በረሃ ላይ ጥሎ መሄድ ራስን ማታለል ነው።

isayaሻዕቢያ ለኢትዮጵያ መጎሳቆል ዋነኛው ተጠያቂ ነው። ገና ከጠዋት የኢትዮጵያ ተማሪዎች የትግል እንቅስቃሴን አቅጣጫ በማወላገድና ኋላም ተራማጁን ክፍል እርስ በእርስ በማጋደል ለኤርትራ ግንጠላ ያዋለው ሻዕቢያ ነበር። ደርግ የሚወጥናቸው ዘመቻዎች ሁሉ እርባና ቢስ የሆኑት ሻዕቢያ እውስጥ በሰገሰጋቸው ሰላዮቹ አማካኝነት ነበር። ኦነግን፣ ኦብነግን ወያኔን ጠፍጥፎ የሠራው ሻዕቢያ ነው። ሻዕቢያ በመጨረሻ እንደ አጋንንት ራሱን ገንጥሎ በረሃ ላይ በረሃብ ይቆዝም ጀመር። ወያኔ መንትያውን ሻዕቢያን አበጥሮ ያውቅ ስለነበር የባድመውን ጦርነት የመጀመርያዋን ጥይት ከመተኮሱ በፊት ሰላዩንና ሰላይ ያልሆነውንም ጭምር አብዛኛውን ኤርትራዊ ከኢትዮጵያ ምድር አባረረ። ጾረናና ዛላንበሳ ግንባር ላይ በቀድሞው ሠራዊትና በወያኔ ሠራዊት ቅንጅት ውጊያ ድል የሆነው፣ ራሱን ክፉኛ የተቀጠቀጠውን እባቡን ሻዕቢያን ሞቷል ብለው ጥለውት ሄዱ። ሻዕቢያ በአስራ አምስተኛው ዓመቱ ግንቦት ሰባት-ኢሳትን ልሶ አሮጌ ቆዳውን ለውጦ የኢትዮጵያ ሕዝብ ፊት በቴሌቪዥን ቀረበ።
ወገኖቼ እባካችሁ እንደገና አንሳሳት። በዚህች ዓለም ፍቅረ ገመድ ታስረን፣ በፍቅረ ሥልጣንና፣ ፍቅረ ንዋይ ተጠምደን ሃገራችንን መከራዋን አናብዛ። እባካችሁ ማስተዋላችንን ለኢትዮጵያ ሃገራችን ትንሳዔ እናውለው። ብዙ መጻፍ አልፈልግም ነገር ግን ይህን፣ የኢትዮጵያ ፖለቲካን ያልገባውን፣ ይህን ኢትዮጵያን አዋራጅ፣ ግንቦት ሰባት-ኢሳትን ማስተማር ስላለንብ ነው ይህችን ትንሺቱን ሃሳቤን የምወረውረው። ዛሬ ለአቶ ኢሳያስ ቃለ መጠይቅ አቅርቦ የይስሙላ ይቅርታ በማስጠየቅ ሻዕቢያ ኢትዮጵያን እንደገና እንዲያፈርስ መንገድ የሚያበጃጀውን ግንቦት ሰባት-ኢሳትን በጽኑ ልንወቅሰው ይገባል።

ለኢትዮጵያ ፖለቲካ መፍትሄው ራሱ የኢትዮጵያ ሕዝብና ከጠላቶቿ ጋር የማያብሩት የፖለቲካ ድርጅቶቿ ብቻ ናቸው። ወያኔንና ግብረአበሮቹን ከሥር መንግለው ኢትዮጵያን ነጻ የሚያወጧት ቆራጦቹ ልጆቿ ናቸው። ሻዕቢያ በኢትዮጵያውያን እግሮች ሥር ተደፍቶ ይቅርታ መጠየቅ ሲገባው እንደ ኦነግና ኦብነግ ጠፍጥፎ በሠራው በሮቦቱ ግንቦት ሰባት-ኢሳት አማላጅነት አይደለም ጀግናው የኢትዮጵያ ሕዝብ ፊት በቴሌቪዥን የሚቀርበው። “ኢትዮጵያን ከጽንፈኞቹ እስላማዊ እንቅስቃሴ ለመጠበቅ ተቃዋሚዎች ከአቶ ኢሳያስ ጋር መናበብና አካባቢውን ማዳን አለባቸው” የሚለው ማደናገርያ የኢትዮጵያ ሕዝብ “ዶሮን ሲያታልሏት” ብሎ ያልፈዋል። የእስላማዊ ጽንፈኝነትን አጀንዳ የሚያራምደው ማን ሆነና ነው አቶ ኢሳያስ የአፍሪካ ቀንዱ ቀጠና ሰላም አስጠባቂ ተደርገው የሚሞካሹት። “እስላማዊ ጽንፈኝነት መጥቶብሃል አቶ ኢሳያስ ጉያ ሥር ተሸሸግ” እያለ የሚያጃጅለው ግንቦት ሰባት-ኢሳት ራሱ ከሕዝብ ቁጣ የሚሸሸግበትን መላ ቢፈልግ ይሻላል።

የኢትዮጵያን ሕዝብ እንደገና በማስተኛትና በማሞኘት በኢትዮጵያ ኪሳራ የኤርትራን በረሃ ውሃ ለማጠጣት ብሎም በአቶ ኢሳያስ የተገደለችውን ኤርትራ ዳግም ነፍስ ለመዝራት መሞከር በቅድስት ኢትዮጵያ ላይ ዳግም የሚሰራ ግፍ ነው። ዋሺንግተን ተራራ ላይ ሆኖ መዋጋቱ አልሆን ቢለው ወደፊት ሊከሰት ይችላል ብሎ የሚመኘውን የሥልጣን ክፍተት ለመሙላት ሻዕቢያን ተገን አድርጎ በመጠባበቅ ላይ ያለው ግንቦት ሰባት-ኢሳት እንደ ቋመጠ ይቀራል እንጂ ከእንግዲህ ሥልጣን ከሕዝብ እጅ አይወጣም። ትግሉ እንኳን ቢዘገይ የኢትዮጵያ ሕዝብ ጸሎት እንደነ አጼ ልብነድንግልና አጼ ገላውድዮስን የመሳሰሉ መሪዎችን ያስነሳል።
ወገኖቼ በአቶ ኢሳያስ መሠርያዊ አነጋገር ዳግም መታለል ለአንድነታችን የታገሉትን ኃይላይ መናቅ ነው። ሻዕቢያን እንደገና ማመን ማለት እምነታችንን መካድ ማለት ነው። ሻዕቢያንና አቶ ኢሳያስን ማዳመጥ ቅኝ ገዥዎችን ያርበደበዱትን የአድዋውን ጀግኖች መዘንጋት ማለት ነው። ሌላው ቀርቶ ኤርትራ ከኢትዮጵያ እንዳትገነጠል ውድ ደማቸውን በኤርትራ በረሃ ላይ ያፈሰሱትን ክቡር አጥንታቸውን በሳህል ምድረ በዳ፣ በናቅፋ ተራሮች፣ በአፋቤት ሜዳዎች ላይ የከሰከሱትን እኚያን ጀግኖች አለማስታወስ እግዚአብሄር የማይወደው የክፋት ሥራ ነውና ዛሬ በግንቦት ሰባት ኢሳት የተቀነባበረውን መሠሪ ሥራ ማውገዝ ይጠበቅብናል።

ፖለቲካ ፌዝ አይደለም። ፖለቲካ ማለት ወያኔን ለማናደድ ሻዕቢያን መጠጋት አይደለም። ፖለቲካ ትላንት አቶ አንዳርጋቸውን ያፈነውን ወያኔን ለማብሸቅ አቶ ኢሳያስን መጨበጥ፣ አስመራ መጓዝ፣ ቃለ ምልልስ ማድረግ፣ ቴምር መመገብ አይደለም። ፖለቲካ በጥበብ የሚደገፍ ትግል ነው። የኢትዮጵያ ፖለቲካ የሃገራችንን ሉዓላዊነቷን ለመመለስ፣ ወያኔ ለባዕዳን የቸረውን መሬቶችና የባህር በር ለማስመለስ፣ ወያኔ በዘር የከፋፈለውን ሕዝቧን ለመታደግ የሚደረግ በሳልና ቆራጥ ትግል ነው። ሃገርን መጠበቅ ጀግኖች አባቶቻችን እንዳስተማሩን ስሜትን ተቆጣጥሮ ብልሃትንና ማስተዋልን መጨበጥ ሃቅን መልበስ ማለት ነው እንጂ የሚላስ የሚቀመስ እሌለበት ሃገር በመመላለስ “የራሱን ምቾቱን ትቶ ቤተሰቡን በትኖ በርሃ ተጓዘ”የሚለውን ተራ ወሬ መንዛት፣ ማስነዛት አይደለም። የተባበሩት መንግስትታ፣ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶችም ሆኑ በጎ አድራጊ ድርጅቶች ሠራተኞቻቸውን ለመስክ ሥራ በረሃ ይልካሉ። ሊታገሉ አይደለም የሚሄዱት። ትግል፣ ለሥልጣን ሳይሆን ለሕዝብ ሲባል ቆራጥ መስዋዕትነት በመክፈል የሚተገበር እንጂ በረሃ መጓዝ ወይም አለመጓዝ አይደለም። በተጋድሏቸውና በድፍረቶቻቸው አርዓያነት ለሕዝብ ነጻነት ፀዳል የሆኑት እነ እስክንድር፣ አንዷዓለም፣ ርዕዮት፣ ኃብታሙ፣ በቀለ ገርባ፣ ዘጠኙ ብሎገሮች፣ ተመስገን፣ ወዘተ የመሳሰሉት የነብር ጣቶች በሠላማዊ መንገድና በአንዲት የብዕር ጠብታ ትግል ምን እንደሚመስል አሳይተዋል።

ይህን ሁሉ ችግር፣ ይህን ሁሉ የኢትዮጵያ አበሳ የፈጠርው ራሱ ወያኔ ነው። ትላንትና እባቡን ሻዕቢያን ራሱን እንደቀጠቀጥነው የሞተ ገላው ዛፍ ላይ ተሰቅሎ ቢቀር ኖሮ ዛሬ ግንቦት ሰባት-ኢሳትን ልሶ አይነሳም ነበር። የእባቡን ሻዕቢያ የተቀጠቀጠ ራስ ሜዳ ላይ ትተነው እንድንሄድ ያደረገን ነገ አፈር ልሶ እንደሚነሳ የሚያውቀው ወንድሙ ወያኔ ነው። ፕሮፌሰር ተስፋጽዮን መድሃኔ “ይኸውና ኤርትራ ሞተች” በሚለው ጥናታዊ ፕሮፖዛላቸው “ወያኔና ሻዕቢያ ተጣብቀው የተወለዱ መንትዬዎች ናቸው” ብለዋል። ግንቦት ሰባት-ኢሳት በሻዕቢያና ወያኔ ማህል ሊገባ አይችልም። መሃላቸው የገባ ከመሰለው ተላላ ነው። ተጣብቀው የተወለዱት ሻዕቢያና ወያኔ አንዱ ከሞተ ያንደኛው ኅልውና ያከትማልና ሁሌም ይጠባበቃሉ። ግንቦት ሰባት-ኢሳት ውስጥ የመሸጋችሁ ተላላ ኢትዮጵያውያን ይህንን ሃቅ ተረድታችሁ ዛሬውኑ “እግሬ አውጭኝ” ብላችሁ ፈርጥጡ።

ኢትዮጵያን በዲሞክራሲ ለማነጽ፣ የወያኔን የተበላሸ የዘር ፖለቲካ ለመገርሰስ አቅሙ ያለው የኢትዮጵያ ሕዝብ ነው። ለኢትዮጵያና ኤርትራ ሕዝብ ዳግም ትስስርም ባለቤቶቹ የኢትዮጵያና የኤርትራ ሕዝቦች ናቸው እንጂ ሻዕቢያ፣ ኦነግ፣ ኦብነግ፣ አልሻባብ አይደሉም። በፕሮፖጋንዳ የሚያግዛቸው ግንቦት ሰባት-ኢሳት በርሃ ላይ ለቆዘመው እባቡ ሻዕቢያ ዳግም እስትንፋስ ሆኗል። ይህ በቀላሉ የሚታይ ስህተት አይደለም። ከዚህ በኋላ ሌላ ሃገርን የሚጎዳ ጥፋት ከመፈጸሙ በፊት ግንቦት ሰባት-ኢሳት ወደ ትክክለኛው የትግል አቅጣጫ እንዲመለስ ምክሬን እለግሳለሁ።

ወያኔና ሻዕቢያ የኢትዮጵያን ትንሳዔ በቅርብ ይመለከታሉ።
አ.ከ. abebekebede321@gmail.com

The post ዕቢያ አፈር ልሶ ተነሳ – ከአበበ ከበደ appeared first on Zehabesha Amharic.

የ2007ቱን ሀገራዊ ምርጫ ሂደት እና ከምርጫዉ ዉጭ ያሉ አዋጭ አማራጮችን በተመለከተ የአርበኞች ግንቦት 7: የአንድነትና ዲሞክራሲ ንቅናቄ የአቋም መግለጫ

$
0
0

አርበኞች ግንቦት 7: የአንድነትና ዲሞክራሲ ንቅናቄ፣ የኢትዮጵያ ሕዝብ በሰላማዊ፣ ተዓማኒና ፍትሀዊ በሆነ ምርጫ የማይፈልጋቸውን መሪዎች መሻር፤ የሚፈልጋቸውን ደግሞ መሾም የሚያስችሉትን መሠረቶች ለመጣል የሚታገል ንቅናቄ ነው። እንደሚታወቀው የሕዝብ እውነተኛ ፍላጎት የሚገለጽበት እውነተኛ ምርጫ እንዲኖር ገለልተኛና ቀልጣፋ የፍትህ ሥርዓት፣ የጦርና የፓሊስ ሠራዊት ሊኖሩ ይገባል። ነፃ የሚዲያ ተቋማትና በነፃነት የሚንቀሳቀሱ የሲቪክ ማኅበራት መኖርም መታለፍ የሌለባቸው አቢይ ጉዳዮች ናቸው። አማራጭ ፓሊሲዎችን ማቅረብ የሚችሉ በነፃነት የሚንቀሳቀሱ የፓለቲካ ፓርቲዎች ከሌሉም አማራጮች የሉምና ምርጫ ትርጉም የለውም። ይህ ሁሉ ቢሟላ እንኳን ምርጫውን የሚያስፈጽመው አካል ገለልተኛ፣ ሀቀኛና ተዓማኒ ካልሆነ የሚደረገው ምርጫ የመራጩን ሕዝብ ፍላጎት የሚያንፀባርቅ ሊሆን አይችልም።

g 7ከላይ የተዘረዘሩትን የምርጫ እሴቶች ሙሉ በሙሉ ባይሆንም እንኳን የተወሰኑትን በመጠኑም ቢሆን ያካተተ ምርጫ እንዲኖር መጣርና በሂደት የምርጫውን አፈፃፀም ማሻሻል ይቻል ይሆናል በሚል እምነት የዲሞክራሲ ኃይሎች በህወሓት የሴራ ምርጫዎች ሲሳተፉ ቆይተዋል። ሆኖም በህወሓትና በእውነተኛ ምርጫ መካከል  ያለው ተቃርኖ እያደር እየሰፋ ሲሄድ እንጂ ሲጠብ አልታየም።  በህወሓት ሙሉ ቁጥጥር ስር በሚካሄድ ምርጫ ኢትዮጵያን የሚጠቅም ለውጥ ሊመጣ ይችላል የሚለው እምነት ለአርበኞች ግንቦት 7 ፈጽሞ የተሟጠጠው ከምርጫ 97 ማግስት ጀምሮ  ነው። በግንቦት 7 ቀን 1997 ዓም የኢትዮጵያ ሕዝብ በታላቅ የለውጥ ተስፋ የሰጠው ድምጽ በህወሓት የተዘረፈው ከላይ የተዘረዘሩት ተቋማት ያልነበሩ በመሆናቸው፤ ስለዚህም ከምርጫ በፊት ተቋማቱን መገንባት፤ ተቋማቱን ለመገንባት ደግሞ ህወሓትን ከስልጣን ማስወገድ ይገባል ብሎ በማመኑ ነው አርበኞች ግንቦት 7 በሁለገብ የትግል ስልት በመንቀሳቀስ ላይ የሚገኘው።

ያም ሆኖ ግን በምርጫ ላይ ያላቸው ተስፋ ፈጽሞ ያልተሟጠጠ ፓርቲዎችን በማክበርና ሥራቸውንም አስቸጋሪ ላለማድረግ ሲባል ከምርጫ 97 ወዲህ የነበሩ ብሄራዊም ሆነ ክልላዊ ምርጫዎችን አስመልክቶ የኢትዮጵያ ሕዝብ ከምርጫ ዉጭ ያሉ ሌሎች አማራጮችን ብቻ እንዲመለከት አርበኞች ግንቦት 7 ጥሪ አድርጎ አያውቅም ነበር። አሁን ግን የአገራችን ኢትዮጵያ የፓለቲካ ሁኔታዎች  ይህንን የቆየ አቋም በሚያስቀይር መንገድ፤ የአገራችንን የወደፊት ዕድል ብቻ ሳይሆን ባጠቃላይ ያካባቢውን ሰላም በሚጎዳ መልኩ ተቀይሯል። የሰሞኑ የወያኔ እርምጃዎች ትንሽ ተስፋ ያደርግ የነበረውን የዴሞክራሲ ወገንተኛ ተስፋም እምሽክ አድርጎ በልቶታል:: እየተቃረበ ያለው ዓይነት የፌዝ ምርጫ ወያኔ እንደ እንጄራ የራበውን የተቀባይነት እጦት ለአጭር ጊዜ ያስታግስለት ይሆናል እንጂ የሀገሪቱን እያደር እየተወሳሰበ የመጣ ችግር ለጊዜውም እንኳን የሚያስታግስ አይሆንም፤ ይልቁንም ጊዜው በገፋ ቁጥር ችግሩ መቋጠሪያ የጠፋው እየሆነ ይሄዳል::

የሁኔታውን አሳሳቢነት ከግምት ውስጥ በማስገባት የአርበኞች ግንቦት 7: የአንድነትና ለዲሞክራሲ ንቅናቄ አመራር የወቅቱን የአገራችን የፓለቲካ ሁኔታ በጥንቃቄ መርምሮ የሚከተሉት ግንዛቤዎች ላይ ደርሷል።

  1. ህወሓት ብዙዎች እትዮጵያዊያን የተሰውላቸውን አንድነት ፓርቲንና መኢአድን በመበተን የድርጅቶቹን ስምና ንብረት ለአገልጋዮቹ መስጠቱ፤ ከዚህ በፊት ሲያደርግ እንደነበረው የመራጭን ድምጽ መስረቅ ሳይበቃው የምርጫ ተወዳዳሪንም መዝረፍ መጀመሩን አመላካች ነው። ይህ ተግባር ህወሓት የምርጫ ውጤትን ብቻ ሳይሆን ተወዳዳሪዎችንም እሱ ራሱ ለመምረጥ መወሰኑን ያሳያል፤ ከዚህ በተጨማሪ የሴራ ምርጫውን ከጅምሩ ጀምሮ አስቀድሞ እስከተወሰነለት መዳረሻው ድረስ ለምንም ዓይነት ያልተጠበቀ አጋጣሚ (በምርጫው ወቅት የሚደረጉትን ክርክር ተብዬዎች ጨምሮ) እድል ላለመስጠት ወስኖ እየተንቀሳቀሰ መሆኑን በግልጽ ያሳያል፤
  2. ይህ እኩይ ውሳኔ በምርጫ ቦርድ ፊርማና አንደበት ቢነገርም ምንጩ የህወሓት ፓሊት ቢሮ  መሆኑን የሚከተሉት ተግባራት ይጠቁማሉ፤

2.1.         በምርጫ ቦርድ በኩል እንዲገለጽ የተወሰነው እርምጃ ለማስመሰል ያክልም ቢሆን የህጋዊነት ሽፋን እንዲኖረው አለመደረጉ ውሳኔው ፍጹም እብሪተኛ በሆነ አካል መወሰኑን ያመለክታል። እንዲህ                   ዓይነቱ እብሪተኛ አካል ደግሞ የህወሓት ፓሊት ቢሮ ነው። ውሳኔውን ለማስፈፀም የነበረው ጥድፊያም ይህንኑ ያጠናክራል።

2.2.        ለማስመሰያ ያክል እንኳን ምንም አይነት የፍርድ ቤት ትዕዛዝ ሳይኖር ፓሊስ የአንድነትና የመኢአድ ቢሮዎችን መውረሩ፤ ህወሓት አንድነትንና መኢአድን አጥፍቶ የድርጅቶቹን ስሞችና ንብረቶች                   ለሚፈልጋቸው ሰዎች ሰጥቶ በአስቸኳይ ለምርጫ ድራማው በፊት መስመር ሊያሰልፋቸው መወሰኑን አመላካች ነው። እንዲህ ዓይነት ከባድ ውሳኔ የሚሰጠው ደግሞ የህወሓት ፓሊት ቢሮ ብቻ                    ነው።

2.3.        ወደ ፈቃድ መንጠቅ ከመደረሱ በፊትም በሰማያዊ ፓርቲ፣ በአንድነትና በመኢአድ አባላት የደረሰው አረመኔያዊ ድብደባ፤ ንቁ የፓለቲካ ተሳትፎ የሚያደርጉ ዜጎች ላይ የሚደርሰው እስር፣ መሰወርና                 እና ባልታወቁ ሰዎች ተገድሎ መገኘት መብዛት እነዚህን አገራዊ ፓርቲዎች የመበተን የፓለቲካ ውሳኔ መሰጠቱን አመላካቾች ናቸው።

  1. ለጊዜው የፈቃድ ነጠቃና የንብረት ዘረፋ የተፈፀመው በአንድነትና በመኢአድ ላይ ቢሆንም በሰማያዊ ፓርቲ ላይ በየእለቱ እየጠነከረ የመጣው የአፈና እርምጃም በተመሳሳይ ፓርቲውን ወደማገድ አለዚያም ፈጽሞ መንቀሳቀስ ወደማይችልበት ደረጃ ሊያደርሰው ይችላል የሚል እምነት አሳድሯል። ሌሎች ፓርቲዎችም ከዚህ ህወሓት ካሰመረው የውሸት ጫወታ መስመር የመውጣት ዝንባሌ ቢያሳዩ ተመሳሳይ እርምጃ አይቀርላቸውም።
  2. የህወሓት የወቅቱ የጥፋት ዒላማ ያነጣጠረው አንፃራዊ በሆነ መንገድ የተሻለ መዋቅርና ማኅበራዊ መሠረት ባላቸው እና በአገራዊ አጀንዳዎቻቸው በሚታወቁ ፓርቲዎች ላይ መሆኑ፤ የወቅቱ የጥፋት ዘመቻ የኢትዮጵያ አንድነትን የማዳከምና ከፋፍሎ የመግዛት የህወሓት ትልቁ አጀንዳ አካል መሆኑን ያሳያል።
  3. እራሱን በዘር ያደራጀዉና ኢትዮጰያ ዉስጥ ያለዉ ፖለቲካዊና ማኅበራዊ አደረጃጀት ከዚሁ እሱ ከተደራጀበት የዘር አደረጃጀት ዉጭ እንዲሆን በፍጹም የማይፈቅደዉ የወያኔ አገዛዝ፤ መጣፊያው ሲያጥረውና ወደ ማይቀረው ውድቀቱ ሲያመራ፤ እኔ ከሞትኩ ሰርዶ አይብቀል እንዳለችው አህያ አገራችን ኢትዮጵያን በቀላሉ ወደማትወጣዉ የዘዉግ ግጭት ዉስጥ አስገብቶ ዘመናት ያስቆጠረዉ አንድነቷ እንዲፈረስ በትጋት እየሠራ መሆኑን ያሳያል።
  4. ከመለስ ዜናዊ ሞት ወዲህ ህወሓት ከሁሉን ጠቅላይ (totalitarian) አገዛዝ ወደ ፋሽስታዊ ቡድንነት ያሽቆለቆለ መሆኑን አርበኞች ግንቦት 7 ተገንዝቧል። ህወሓት ዘረኛ፣ ጠቅላይና ፈላጭ ቆራጭ ጨቌኝ በመሆኑ ፋሽስት ብለነዋል።  ሆኖም በታሪክ የሚታወቁ ፋሺስታዊ አገዛዞች ከፍተኛ ብሄራዊ ስሜት የነበራቸው ሲሆን የህወሓት ፋሽስታዊ አገዛዝ ግን ብሔራው ስሜት አልባ መሆኑ ልዩ እና የበለጠ አደገኛ ያደርገዋል። ይህ ፋሽስታዊ ቡድን የህወሓት መሪዎችንና ጥቂት ሌሎች አጫፋሪዎቻቸውን የያዘ ለጊዜው አስተባባሪ መሪ የሌለው ሆኖም ግን የጦር ሠራዊትን፣ የስለላ መዋቅሩንና ፓሊስን ተቆጣጥሮ በአሁኑ ሰዓት ኢትዮጵያን እየገዛ ያለው ይህ አስኳል የለሽ ፋሽስታዊ ቡድን መሆኑ እጅግ አሳሳቢ ጉዳይ መሆኑን አርበኞች ግንቦት 7 ተገንዝቧል። ይህ ፋሽስታዊ ቡድን ተደላድሎ መሪ እንዲፈጥር ከተፈቀደለት አገራችንን የከፋ መከራ ውስጥ ሊከታት እንደሚችል ግንዛቤ ተወስዷል።

 

ከላይ በአጭሩ ከተራ ቁጥ 1 እስከ 6 የተዘረዘሩትን በማገናዘብ በግንቦት 2007 ሊደረግ የታቀደውን አምስተኛው ዙር ሀገር አቀፍ የሴራ ምርጫን በተመለከተ የአርበኞች ግንቦት 7 አመራር ውሳኔዎችን አስተላልፎ ከዚህ የሚከተሉት ጥሪዎችን ለኢትዮጵያ ሕዝብ አቅርቧል።

  1. በምርጫ 2007 መሳተፍ ለዲሞክራሲያዊ ለውጥ ሁኔታዎችን ከማመቻቸት ይልቅ ፋሽስታዊውን ቡድን የሚያጠናክርና የኢትዮጵያን ሕዝብ የወደፊት ዕድል የሚገድል በመሆኑ፣ ለፍትህ፣ ለነፃነት፤ ለዲሞክራሲና ለአገር አንድነት ግድ ያላቸው ወገኖች ሁሉ ከአሁኑ ከዚህ የይስሙላ ምርጫ ዉጭ ዓይኖቻቸውንና ሙሉ ጉልበታቸዉን በሌሎች የኢትዮጵያን ሕዝብ ነፃነት በሚያፋጥኑ አማራጮች ላይ እንዲያሳርፉ ጥሪ ያደርጋል። አርበኞች ግንቦት 7 የኢትዮጵያ ሕዝብ ከዚህ ዓይን ያወጣ የሴራ ምርጫ ይልቅ መብቱን፤ ነፃነቱንና እኩልነቱን በሚያፋጥኑለት በሕዝባዊ እምቢተኝነትና በሕዝባዊ አመፅ የትግል አመራጮች ላይ እንዲሳትፍ ለመላው ያገሪቱ ሕዝብ ጥሪ ያስተላልፋል።  ህወሓት ማኅበረሰባችንን ለመከፋፈልና ለማባላት የሚያደርገውን እኩይ ሴራ በጋራ እንድናከሽፈው ወገናዊ ጥሪ ያስተላልፋል፤ “አንከፋፈልም፤ ተከፋፍለንም አንጠቃም“ እንበል ይላል::
  2. ህወሓትን ማስወገድ የሚቻለው በሕዝባዊ እምቢተኝነትና በሕዝባዊ አመጽ በመሆኑ፤  ከሁለቱ አንዱንም አለመያዝ ሌላ ሰው ታግሎ ነፃነቴን ያቀዳጀኝ እንደማለት የሚቆጠር በመሆኑ፤ እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ በአፋጣኝ ከእነዚህ ሁለት የትግል ዘርፎች ዉስጥ የተሻለ አስተዋጽኦ አበረክታለሁ በሚለው የትግል ዘርፍ ውስጥ ተሳትፎ  እንዲያደርግ ጥሪ ያቀርባል።
  3. አርበኞች ግንቦት 7፣ በሁለቱም የትግል ዘርፎች ድርጅታዊ መዋቅሩን እያሰፋና ከሌሎች ድርጅቶች ጋር በመተባበር በሕዝባዊ እምቢተኝነትና በሕዝባዊ አመጽ ህወሓትን ከስልጣን ለማስወገድ አቅዶ በመንቀሳቀስ ላይ የሚገኝ በመሆኑ ኢትዮጵያዊያን በስፋት እንዲቀላቀሉት፤ በኅብረት እንድንቆም እና የህወሓትን ውድቀትና የኢትዮጵያን ትንሳኤ እንድናፋጥን ጥሪ ያደርጋል::
  4. ያለንን አቅም በሙሉ ህወሓትን በማስወገድ ላይ ካዋልነው አንድ ጠንክር ያለ ሕዝባዊ አመጽ አገዛዙን ሊያፍረክርክው የሚችል በመሆኑ፤ በአንድ ወይም በሌላ መንገድ ከምርጫ ጋር ለተያያዙ ሥራዎች ሊውል ታስቦ የነበረው የሰው ኃይል፣ ጊዜ፣ ገንዘብና እውቀት ለሕዝባዊ አብዮት መቀስቀሻነት እንዲውል ጥሪ ያደርጋል።
  5. በውጭ አገራት የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ወገኖቻችንም በ2007 ምርጫ ላይ ጊዜና ንብረት ከማባከን ይልቅ በአንድ ልብ በኢትዮጵያ ውስጥ ለሕዝባዊ አብዮት መቀስቀስ የበኩላቸውን አስተዋጽኦ እንዲያደርጉ ጥሪ ያደርጋል።   ከሁሉም ዴሞክራሲያዊ ኃይሎች የተውጣጣ አካል የዚህን ጥሪ ተፈፃሚነት እንዲከታተል ቢደረግ ይበልጥ ውጤታማ ይሆናል ብሎ ያምናል።

The post የ2007ቱን ሀገራዊ ምርጫ ሂደት እና ከምርጫዉ ዉጭ ያሉ አዋጭ አማራጮችን በተመለከተ የአርበኞች ግንቦት 7: የአንድነትና ዲሞክራሲ ንቅናቄ የአቋም መግለጫ appeared first on Zehabesha Amharic.

“እንኩሃንም ከናንተ ጓሮ በቀልኩ!” –የጐንቻው


ምርጫ ቦርድ ከ200 በላይ የሰማያዊ ፓርቲ ዕጩዎችን ሰረዘ

$
0
0

• ‹‹ምርጫ ቦርድ ሰማያዊ በምርጫ ሂደቱ እንዲቆይ አይፈልግም›› ኢ/ር ይልቃል ጌትነት

blue partyሰማያዊ ፓርቲ በተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች ከ200 በላይ ዕጩዎቹ በምርጫ ቦርድ ትዕዛዝ እንደተሰረዙበት የፓርቲው ሊቀመንበር ኢ/ር ይልቃል ጌትነት ለነገረ ኢትዮጵያ ገለጹ፡፡ ሰማያዊ ፓርቲ በመላ አገሪቱ በተለይም በደቡብ ወሎ፣ በሰሜን ሸዋ፣ በወላይታ፣ በቤንች ማጅ፣ በምዕ/ጎጃም፣ በሲዳማ፣ በከምባታ፣ በጋሞጎፋ፣ አዲስ አበባ፣ በደቡብ ጎንደርና ጉጅን ጨምሮ በሌሎችም የአገሪቱ ክፍሎች ከ200 በላይ ዕጩዎቹ አንድን ዕጩ ለመሰረዝ የሚያበቃ ምንም አይነት ህጋዊ ምክንያት ሳይኖር ‹‹ከብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በደብዳቤ ታዘናል›› በማለት ለህዝብ ተወካዮች ምክርቤትና ለክልል ምክር ቤቶች ያስመዘገብናቸው ዕጩ ተወዳዳሪዎቹን በመሰረዝ ከምርጫው ውድድር ውጪ እንዲሆኑ እየተደረገ እንደሆነ ኢንጅነር ይልቃል ጌትነት ገልጸዋል፡፡

በየክፍለ ሀገሩ የተሰረዙት ዕጩዎች ‹‹ፓርቲው ትብብር የሚባል ህገ ወጥ አደረጃጀት መስርቷል፣ የሌሎች ፓርቲዎች አባላት ናችሁ›› የመሳሰሉ ምክንያቶችና ደብዳቤ የተሰጣቸው ሲሆን በአንጻሩ በአዲስ አበባ የተሰረዙት ዕጩዎች ከምርጫ አስፈጻሚዎች ምንም አይነት ምክንያትና ደብዳቤ እንዳልተሰጣቸው ለማወቅ ተችሏል፡፡ ዕጩዎቹ ‹‹የተሰረዝንበትን ምክንያት ንገሩን፣ ደብዳቤ ልትሰጡን ይገባል›› ቢሉም የምርጫ አስፈጻሚዎቹ ‹‹እኛ እናንተን ለመመዝገብ ችግር የለብንም፡፡ ግን ከበላይ አካል እንዳንመዘግብ ተነግሮናል፡፡ ደብዳቤም ልንሰጣችሁ አንችልም፡፡›› የሚል መልስ እንደሰጧው ተግልጾአል፡፡

በተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች የሰማያዊ ፓርቲ ዕጩዎች መሰረዛቸውን ተከትሎ የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮች የቦርዱን ሰብሳቢ ፕ/ር መርጋ በቃናን ለማግኘት ቢጥሩም ‹‹ከከተማ ውጭ ናቸው፡፡ አሁን አታገኟቸውም›› የተባሉ ሲሆን ፕ/ር መርጋ የህወሓትን 40ኛ አመት ለማክበር መቀሌ መሆናቸው ታውቋል፡፡ ኢ/ር ይልቃል ጌትነት በትናንትናው ዕለት በጉዳዩ ላይ ከቦርዱ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ነጋ ዱፌሳ ጋር የተነጋገሩ ሲሆን አቶ ነጋ ‹‹ማመልከቻ አስገቡ›› ከማለት ውጭ ዕጩዎቹ ለመሰረዛቸው ተጨባጭ ምክንያት መስጠት እንዳልቻሉ ኢ/ር ይልቃል ገልጸውልናል፡፡

‹‹የሰማያዊ ፓርቲ ዕጩዎችን ያለ አግባብ የሚሰርዙት ሰማያዊ በምርጫ ሂደቱ ጫና መፍጠር ስለሚችል በሂደቱ እንዲቆ ስለማይፈልጉ ነው›› ያሉት ኢንጅነር ይልቃል ጌትነት፤ ሆኖም ይህ የምርጫ ቦርድ ውሳኔ ለነጻነት የሚያደርጉትን ትግል ትክክለኛ እንደሆነ እንዳስረገጠላቸው፣ ይህን የነጻነት ትግልም አጠናክረው እንደሚቀጥሉና የካቲት 22 ፓርቲያቸው ከትብብሩ ፓርቲዎች ጋር በ15 ከተሞች በተመሳሳይ ጊዜ በ15 ከተሞች የሚያደርገው ሰልፍ የዚሁ የነጻነት ትግል አካል እንደሆነ ገልጸዋል፡፡

The post ምርጫ ቦርድ ከ200 በላይ የሰማያዊ ፓርቲ ዕጩዎችን ሰረዘ appeared first on Zehabesha Amharic.

ለቅሶ በራፍ ፍርድ ቤት ( የልጅና የአባት መተያየት) –ለገሰ ወልደሃና

$
0
0

 

zemeneዘመነ ምህረት እና መለሰ መንገሻ ከተያዙ አንድ ወር ከአንድ ቀን ሆናቸው በዛሬው እለት ፍርድ ቤት ይቀርባሉ ተብሎ የመኢአድ አባላት እና ይህ በፎቶ የምታዩት አንድነት ዘመነ ከእናቱ ጋር ከሰሜን ጎንደር ሌሎችም የዘመነ ቤተሰብም ተገኝተዋል ዘመነ የመኢአድን ጠቅላላ ጉባኤ ተካፍሎ ከተመለሰ በኋላ አላገኘነውም አይኑን ለማየት ጉጉተናል የተባለው ሰአት 8:00 ደረሰና ከእሱ ጋር የታሰረው መለሰ መንገሻም አብረው በጋቴና ሌሎች ወደ 25 የሚጠጉ ወጣቶች በፓሊስ ታጅበው ገቡ በእርቀት እጃችን በማወዛወዝ ሰላም አልናቸው እነሱ ባልታሰረው እጃቸው መለሱልን ። በጣም ተጎሳቁለዋል በተለይ መለሰ ግርጥት ብሏል፤ተአምረኛው አንድነት ።

አንድነት የዘመነ የበኩር ልጅ ነው። እድሜውም 3 አመት ከአራት ወር ነው። ሲበዛ ያሳዝናል ። አባቱ ዘመነ፣ ከበርካታ ታሳሪዎች ጋር ወደ ፍርድ ቤት ሲገባ አባቱን ያየው አንድነት፣ ከእጄ አምልጦ ወደ አባቱ ሮጠ። አባቱን ግን አላገኘም። አባቱን ለማቀፍ የሮጠው ልጅ፣ ከፓሊሱ አልፎ አባቱን ሊያቅፍ አልቻለም። ቀድሞም ይህ ህጻን አይኑ እያየ አባቱን እየደበደቡ የወሰዱት ፓሊሶች ነበሩና የማይጋፋው ጉልበተኛ እንደገጠመው አውቋል።

ያችን ቅጽበት ሁሌ የምረሳው አይደለም። አንድነት አራዳን በጩኸት አቀለጣት። ዘመነን ለማየት የጓጓው አይናችን ዘመነን እረሳ። ተሸነፍን። እንባችን ግድቡን ጥሶ ፈሰሰ። አንዳንድ የመኢአድ አባላት በህጻኑ አንድነት ልባቸው ተነክቶ ድምጻቸው ከፍ ብሎ እስኪሰማ አለቀሱ። በግቢው የነበሩ ባለጉዳዮችም ሲያለቅሱ ተመልክቻለሁ ። እንዴት ልብ ይነካል ።

ዘመነ ምን ተሰምቶት ይሆን ? በዚህ ክስተት መሀል ዘመነን ባይኔ ፈለኩት። ሌሎች ያለቅሳሉ ። ዘመነ ግን ከአይኑ የሚፈስ እንባ የለም የሆነውን አይቷል። እንዴት አንጀቱ ቻለው ? ዘመነ ልጁን እንዴት እንደሚወደው አውቃለሁ ። ዛሬ እንዴት ቻለው? ምን አልባት እንባን ያላየሁት ወደ ውስጥ እያለቀሰ ይሆን ?

The post ለቅሶ በራፍ ፍርድ ቤት ( የልጅና የአባት መተያየት) – ለገሰ ወልደሃና appeared first on Zehabesha Amharic.

ምርጫ ቦርድ ከ200 በላይ የሰማያዊ ፓርቲ ዕጩዎችን ሰረዘ

$
0
0

• ‹‹ምርጫ ቦርድ ሰማያዊ በምርጫ ሂደቱ እንዲቆይ አይፈልግም›› ኢ/ር ይልቃል ጌትነት

Yilkalሰማያዊ ፓርቲ በተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች ከ200 በላይ ዕጩዎቹ በምርጫ ቦርድ ትዕዛዝ እንደተሰረዙበት የፓርቲው ሊቀመንበር ኢ/ር ይልቃል ጌትነት ለነገረ ኢትዮጵያ ገለጹ፡፡ ሰማያዊ ፓርቲ በመላ አገሪቱ በተለይም በደቡብ ወሎ፣ በሰሜን ሸዋ፣ በወላይታ፣ በቤንች ማጅ፣ በምዕ/ጎጃም፣ በሲዳማ፣ በከምባታ፣ በጋሞጎፋ፣ አዲስ አበባ፣ በደቡብ ጎንደርና ጉጅን ጨምሮ በሌሎችም የአገሪቱ ክፍሎች ከ200 በላይ ዕጩዎቹ አንድን ዕጩ ለመሰረዝ የሚያበቃ ምንም አይነት ህጋዊ ምክንያት ሳይኖር ‹‹ከብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በደብዳቤ ታዘናል›› በማለት ለህዝብ ተወካዮች ምክርቤትና ለክልል ምክር ቤቶች ያስመዘገብናቸው ዕጩ ተወዳዳሪዎቹን በመሰረዝ ከምርጫው ውድድር ውጪ እንዲሆኑ እየተደረገ እንደሆነ ኢንጅነር ይልቃል ጌትነት ገልጸዋል፡፡

በየክፍለ ሀገሩ የተሰረዙት ዕጩዎች ‹‹ፓርቲው ትብብር የሚባል ህገ ወጥ አደረጃጀት መስርቷል፣ የሌሎች ፓርቲዎች አባላት ናችሁ›› የመሳሰሉ ምክንያቶችና ደብዳቤ የተሰጣቸው ሲሆን በአንጻሩ በአዲስ አበባ የተሰረዙት ዕጩዎች ከምርጫ አስፈጻሚዎች ምንም አይነት ምክንያትና ደብዳቤ እንዳልተሰጣቸው ለማወቅ ተችሏል፡፡ ዕጩዎቹ ‹‹የተሰረዝንበትን ምክንያት ንገሩን፣ ደብዳቤ ልትሰጡን ይገባል›› ቢሉም የምርጫ አስፈጻሚዎቹ ‹‹እኛ እናንተን ለመመዝገብ ችግር የለብንም፡፡ ግን ከበላይ አካል እንዳንመዘግብ ተነግሮናል፡፡ ደብዳቤም ልንሰጣችሁ አንችልም፡፡›› የሚል መልስ እንደሰጧው ተግልጾአል፡፡

በተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች የሰማያዊ ፓርቲ ዕጩዎች መሰረዛቸውን ተከትሎ የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮች የቦርዱን ሰብሳቢ ፕ/ር መርጋ በቃናን ለማግኘት ቢጥሩም ‹‹ከከተማ ውጭ ናቸው፡፡ አሁን አታገኟቸውም›› የተባሉ ሲሆን ፕ/ር መርጋ የህወሓትን 40ኛ አመት ለማክበር መቀሌ መሆናቸው ታውቋል፡፡ ኢ/ር ይልቃል ጌትነት በትናንትናው ዕለት በጉዳዩ ላይ ከቦርዱ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ነጋ ዱፌሳ ጋር የተነጋገሩ ሲሆን አቶ ነጋ ‹‹ማመልከቻ አስገቡ›› ከማለት ውጭ ዕጩዎቹ ለመሰረዛቸው ተጨባጭ ምክንያት መስጠት እንዳልቻሉ ኢ/ር ይልቃል ገልጸውልናል፡፡

‹‹የሰማያዊ ፓርቲ ዕጩዎችን ያለ አግባብ የሚሰርዙት ሰማያዊ በምርጫ ሂደቱ ጫና መፍጠር ስለሚችል በሂደቱ እንዲቆ ስለማይፈልጉ ነው›› ያሉት ኢንጅነር ይልቃል ጌትነት፤ ሆኖም ይህ የምርጫ ቦርድ ውሳኔ ለነጻነት የሚያደርጉትን ትግል ትክክለኛ እንደሆነ እንዳስረገጠላቸው፣ ይህን የነጻነት ትግልም አጠናክረው እንደሚቀጥሉና የካቲት 22 ፓርቲያቸው ከትብብሩ ፓርቲዎች ጋር በ15 ከተሞች በተመሳሳይ ጊዜ በ15 ከተሞች የሚያደርገው ሰልፍ የዚሁ የነጻነት ትግል አካል እንደሆነ ገልጸዋል፡፡

The post ምርጫ ቦርድ ከ200 በላይ የሰማያዊ ፓርቲ ዕጩዎችን ሰረዘ appeared first on Zehabesha Amharic.

ለመሆኑ ለወደፊቱ የየካቲት ፲፪ ቀን ፲፱፻፳፱ ዓ.ም. ሠማዕታትን የሚዘክር ተተኪትውልድ ይኖረን ይሆን?

$
0
0

Moreshኢትዮጵያውያን በታሪክ በተለያዩ ዘመኖች ከውጭ ወራሪዎች ጋር ተፋልመዋል። ሁሉም የውጭ ወራሪዎች ዘለቄታዊ ግባቸው ተመሣሣይ ነበር፦ ኢትዮጵያን ቅኝ ግዛታቸው አድርገው ሕዝቧን በባርነት ቀንበር ሥር መግዛት። በዚህ ረገድ አረቦች ከ፰ኛው (ስምንተኛው) መቶ ክፍለዘመን ጀምሮ በእስልምና ኃይማኖት ማስፋፋት ሽፋን ተደጋጋሚ ወረራ ፈፅመዋል። ቱርኮችም በአረቦች እግር ተተክተው ከ፲፮ኛው (አሥራ ስድስተኛው) መቶ ክፍለ-ዘመን መግቢያ ጀምሮ በኢትዮጵያ ላይ በተደጋጋሚ ከሰሜን-ምዕራብ እና ከሰሜን አቅጣጫ በሱዳን፣ ከሰሜን-ምሥራቅ አቅጣጫ በቀይባሕር፣ እንዲሁም ከምሥራቅ እና ደቡብምሥራቅ አቅጣጫ ግራኝ አሕመድን በጦር ኃይል ድጋፍ እየሰጡ በግማሽ ቀለበት ኢትዮጵያን የከበበ ወረራ አካሂደው ነበር። የቱርኮች ወረራ ያከተመው አዳዲሶቹ ቅኝ ገዢዎች እንግሊዝ፣ ፈረንሣይ እና ጣሊያን በ፲፱ኛው (አሥራ ዘጠነኛው) መቶ ክፍለዘመን አጋማሽ ጀምሮ ሲተኩ ነበር። ሆኖም ቱርኮች በኢትዮጵያውያን ላይ ትተውት የሄዱት የጥፋት ጠባሣ እስካሁን ድረስ አልጠፋም። በዳግማዊ አፄ ቴዎድሮስ ዘመን በ፲፰፻፷ (1860) ዓ.ም. እንግሊዞች «የታሠሩብንን እስረኞች እናስፈታለን» በሚል ሠበብ በኢትዮጵያ ላይ ጦርነት አወጁ። በወቅቱ ከኢትዮጵያ መሣፍንት መካከል ለእንግሊዞች ወረራ ቀጥተኛ ድጋፍ ያደረጉት ጥሶ ጎበዜ (በኋላ አፄ ተክለጊዮርጊስ) እና ካሣ ምርጫ (በኋላ አፄ ዮሐንስ ፬ኛ) ነበሩ። የእንግሊዞች ወረራ ዓላማ እሥረኛ ማስፈታት ስላልነበረ፣ ዳግማዊ አፄ ቴዎድሮስ በብዙ ድካም ያሰባሰቡትን ልዩ ልዩ ቅርስ የዘረፉትን ዘርፈው፣ አብዛኛውን አቃጥለው እና አውድመው ተመለሱ። እንግሊዞች ቆዬት ብለውም በአፄ ዮሐንስ ፬ኛ ዘመን ጣሊያኖች በቀይ ባሕር ዳርቻ ግዛት እንዲያገኙ እና ምፅዋን እንዲቆጣጠሩ አደረጉ፤ በኢትዮጵያም ላይ መሠሪ ጠላት ተከሉባት። እስከዛሬም ድረስ እንግሊዞች በኢትዮጵያ ላይ ያላቸውን የጠላትነት ፖሊሲ አልሰረዙም።

ኢትዮጵያውያን ከጣሊያኖች ጋር ሁለት ጊዜ ተዋግተዋል፦ በመጀመሪያ በ፲፰፻፹፰ (1888) ዓ.ም. በአድዋ ሲሆን ከዚያም ከ፵(አርባ) ዓመታት በኋላ ለ፭(አምሥት) ዓመታት ከ፲፱፻፳፰ – ፲፱፻፴፫ (1928 – 1933) ዓ.ም.። ጣሊያኖችን በአድዋ ድል የነሣቸው በታላቁ የኢትዮጵያ ንጉሠ-ነገሥት በዳግማዊ አፄ ምኒልክ የተመራው የኢትዮጵያ ጀግኖች ሠራዊት ነበር። ጣሊያኖች፣ እና በአጠቃላይም ቅኝ ገዢዎች፣ የአድዋን ድል ጠባሣ ለመፋቅ ለ፵(አርባ) ዓመታት ቂም ቋጥረው፣ አስፈላጊውን ዝግጅት ሁሉ አድርገው ሲያበቁ በቤኔቶ ሙሶሎኒ በሚመራው የፋሽስት ጦር ኢትዮጵያን ፲፱፻፳፰ (1928) ዓ.ም. ዳግም ወረሩ። በ፭(አምስቱ) ዓመት ወረራ ፋሽስቶች ከአንድ ሚሊዮን የማያንሱ ኢትዮጵያውያንን ጨፍጭፈዋል። በተለይም በየካቲት ፲፪/፲፱፻፳፱ (12/1929) ዓ.ም. በአዲስ አበባ እና በአካባቢዋ ያደረሱት የግፍ ግድያ በታሪካችን ካጋጠሙን ዘግናኝ የጭፍጨፋ ድርጊቶች የሚስተካከሉት በግራኝ ዘመን እና አሁን በትግሬ-ወያኔ የአገዛዝ ዘመኖች የተፈጸሙት እና የሚፈጸሙት ናቸው።

የውጪ ወራሪ ኃይሎች በጣሊያኖች ፊታውራሪነት ሁለት ጊዜ ሲወርሩን ከመጀመሪያው በሁለተኛው የበለጠ ጉዳት እንዳደረሱብን ግልፅ ነው። ሆኖም የውጭ ኃይሎች በቀጥታ ወረራ ኢትዮጵያን ሙሉ በሙሉ ቅኝ ለማድረግ እንዳልቻሉ ተገንዝበዋል። ስለዚህ በፋሽስት ዘመን በመለመሏቸው ባንዳ ሎሌዎቻቸው አማካይነት ኢትዮጵያን ለዘለቄታው ለማፈራረስ የሚስችላቸውን ተተኪ ዕቅድ ነድፈው ተግባራዊ ማድረግ ቀጠሉ። ለ፶(ሃምሣ) ዓመታት በአገር-በቀል ባንዶች በእነ ሻቢያ፣ ትግሬ-ወያኔ፣ ኦነግ፣ ኦብነግ፣ ሲዳማ አርነት ንቅናቄ፣ ወዘተርፈ አማካይነት በመጠቀም በአዲስ ዘይቤ ኢትዮጵያን ገዝግዘው፣ በ፲፱፻፹፫ (1983) ዓ.ም. አገራችንን ለመቆጣጠር በቅተዋል። ስለሆነም ላለፉት ፳፬(ሃያ አራት) ዓመታት ኢትዮጵያን ለሁለት ከፍለው የሚገዟት ሻቢያ እና የትግሬ-ወያኔ የሚያከናውኗቸው ተግባሮች ሁሉ ጌቶቻቸው የውጭ ኃይሎች የሠጧቸውን መመሪያ ተከትለው እንደሆነ ለአፍታም ሊዘነጋ አይገባም።

ልክ የዛሬ ዓመት በዚህ ዕለት ሞረሽ ወገኔ አንድ ወቅታዊ መግለጫ አውጥቶ ነበር፦ «የየካቲት ፲፪ ሠማዕታትን ስናስብ» የሚል። ከአንድ ዓመት በኋላ ሁኔታው ሲታይ፣ ኢትዮጵያውያን እንኳን ለእንደዚህ ዓይነቱ ጥሪ ተግባራዊ ምላሽ ሊሠጡ ቀርቶ፣ በተቃራኒው የትግሬ-ወያኔዎች የጥፋት ድርጊት ይበልጥ ተስፋፍቶ ይታያል። የእኛ የኢትዮጵያውያኑ ዝምታ እና ምንቸገረኝነት እንኳን ሕያዋንን ሙታንን ያስደነግጣል። ለመሆኑ በዚህ ዓይነት ቸልተኝነት ለተተኪው ትውልድ ምን እያወረስነው ነው? በዚህ ከቀጠልንስ ከተተኪው ትውልድ መካከል የየካቲት ፲፪ ቀን ፲፱፻፳፱ ዓ.ም. ሠማዕታትን የሚዘክር ይኖረን ይሆን? ብሎ መጠየቅ አግባብነት ይኖረዋል። ስለሆነም ቸልተኝነቱ ይብቃ! ሠማዕቶቻችንን እናስብ፣ ለእነርሱም ተገቢውን ክብር እንስጥ!

– See more at: http://satenaw.com/amharic/archives/4771#sthash.3PaVn2ym.dpuf

The post ለመሆኑ ለወደፊቱ የየካቲት ፲፪ ቀን ፲፱፻፳፱ ዓ.ም. ሠማዕታትን የሚዘክር ተተኪትውልድ ይኖረን ይሆን? appeared first on Zehabesha Amharic.

Health: ስለ እርግዝና መከላከያዎች 10 ነጥቦች

$
0
0

(በዶ/ር ሆነሊያት ኤፍሬም ቱፈር)

ያልተፈለገ እርግዝናን ለመከላከልና ራስዎን ከአባላዘር በሽታዎች ለመጠበቅ ሲባል የተለያዩ መንገዶችን ይጠቀሙ ይሆናል፡፡ ነገር ግን የእነዚህን መከላከያዎች እውነታዎች አውቆና ተረድቶ ጥቅም ላይ ማዋል እጅግ ጠቀሜታ ይኖረዋል ብዬ ስለማስብ ይህን ጽሑፍ አዘጋጅቼላችኋለሁ፡፡

pregnant test
1) በወር አበባ ጊዜ የግብረ ሥጋ ግንኙነት ቢደረግ እርግዝና ይከሰት ይሆን?

የወር አበባን የምታይ ጊዜ የግብረ ሥጋ ግንኙነት ሴት የማርገዝ ዕድሏ የቀነሰ ቢሆንም ሙሉ በሙሉ ግን አይከሰትምለማለት አይቻልም፡፡ ይህም የሚሆንበት ምክንያት የወር አበባ ከማለቁ በፊት እንቁላል ሊፈጠር ስለሚችልና ወይንም ደግሞ የወንድ ዘር በማኅፀን ውስጥ እስከ 3 ቀን ወይንም ከዚያ በላይ የሚቆይበት አጋጣሚ ስለሚኖር ነው፡፡

2) ጡት ማጥባት እርግዝናን ይከላከላል?

ጡት ማጥባት የእንቁላል መፈጠርን የሚከላከል ቢሆንም የሚቆይበት ጊዜ ግን ለጥቂት ወራት ብቻ ስለሆነ ሰውነት ወደቀድሞ ሁኔታው በሚመለስ ጊዜ የማርገዝ ዕድልም አብሮ ስለሚመለስ ጡት ማጥባት እርግዝናን የሚከላከልብት ጊዜ ውስን መሆኑን መገንዘብ ያስፈልጋል፡፡

3) የመጀመሪያ ጊዜ የግብረ ሥጋ ግንኙነት ማድረግ ላልተፈለገ እርግዝና ያጋልጣል?

አዎን! ለመጀመሪያ ጊዜ የሚደረግ የግብረ ሥጋ ግንኙነት ላልተፈለገ እርግዝና ላያጋላጥ ይችላል ብለው የሚያስቡ አንዳንዶች ያሉ ቢሆንም ይህ ከእውነት የራቀ ነው፡፡ በመጀመሪያ የግብረ ሥጋ ግንኙነት ወቅት ሕመምና ደም መፍሰስ ሊያጋጥም የሚችል ቢሆንም እርግዝናን ከመከላከል ጋር ግን ምንም ዓይነት ግንኙነት የሌለው መሆኑን ተገንዝቦ ተገቢውን ጥንቀቄ ማድረግ ያስፈልጋል፡፡

4) የወሊድ መቆጣጠሪያዎች ምን ያህል እርግዝናን ይከላከላሉ?

የወሊድ መቆጣጠሪያዎች በትክክለኛው መንገድ ከተተገበሩ ከ90% በላይ የሚሆን የመከላከያ አቅም ያላቸው ሲሆን ተአቅቦ ግን ጥርጥር የሌለው አማራጭ ነው፡፡ የወሊድ መቆጣጣሪያ ለመጠቀም በሚታሰብ ጊዜ የትኛውን ዓይነት እንደምንመርጥና አጠቃቀሙን በተመለከተ ሐኪምዎን ማማከር ተገቢ ነው፡፡

5) በግብረ ሥጋ ግንኙነት ጊዜ ሁለት ኮንዶሞች ደርቦ መጠቀም በእርግጥ እርግዝናን የበለጠ ይከላከላል?

አብዛኛውን ጊዜ ሰዎች ሁለት ኮንዶምን ደርቦ በመጠቀም የበለጠ ጠቀሜታ እንዳለው ያስባሉ ይህ ግን እጅግ የተሳሳተ እና ከእውነት የራቀ ሲሆን ይባስ ብሎ በሚፈጠረው ፍጭት (Friction) ምክንያት የኮንዶም መቀደድ በማስከተል ላልተፈለገ እርግዝና ለአባላዘር በሽታ የመጋለጥን ዕድል በከፍተኛ ሁኔታ ይጨምራል፡፡ ስለዚህ ሁለት ኮንዶሞችን ደርቦ መጠቅም አይመከርም፡፡

6) የወሊድ መቆጣጠሪያ እንክብሎችን መውሰድ ወዲያውኑ እርግዝናን ይከላከላል?

የወሊድ መቆጣጠሪያ እንክብሎች አጠቃቀም እና የሚወሰዱበትን ጊዜ በሚገባ ማወቅ እርግዝናን ለመከላከል ጠቃሚ ነው፡፡ የወሊድ መቆጣጠሪያ እንክብሎችን የወር አበባ በመጣ ከመጀመሪያው ቀን እስከ አምስተኛው ቀን ውስጥ መጀመር ወዲውኑ ከአልተፈለገ እርግዝና የሚከላከል ሲሆን፣ ከዚያ ጊዜ ውጭ ከመጀመሩ ግን ወዲያውኑ የመከላከል አቅም ስለማይኖረው ኮንዶምን መጠቀም አስፈላጊ ይሆናል፡፡

7) ሁሉም የወሊድ መቆጣጠሪያዎች ከአባለዘር በሽታዎች ይከላከሉ ይሆን?

ከወሊድ መቆጣጠሪያዎች ውስጥ ኮንዶምን መጠቀም ብቻ ከአባላዘር በሽታ ራስን መከላከል የሚቻልበት ዋነኛው መንገድ ነው፡፡

8) የወሊድ መቆጣጠሪያ እንክብሎች የሰውነት ክብደት ይጨምራሉ?

አንዳንድ ሴቶች የሰውነት ክብደት መጨመርን እንዳስከተለባቸው የሚናገሩ ሲሆን ምክንያቱም የምግብ ፍላጎትን መጨመርን ማስከተሉና ፈሳሽ በሰውነታችን እንዲቀመጥ ማድረጉ መሆኑን ጥናቶች ያሳያሉ፡፡ ስለዚህም የወሊድ መቆጣጠሪያ እንክብሎች መጠነኛ የሚባል የሰውነት ክብደት መጨመርን ያስከትላሉ፡፡

9) የወሊድ መቆጣጠሪያን መጠቀም መሃንነትን ያስከትላል?

አያስከትልም! ሆርሞኖችን በውስጣቸው የያዙ የወሊድ መቆጣጠሪያዎች ለረጅም ጊዜ ከተወሰዱ መሃንነትን ያስከትላሉ ተብሎ የሚታሰብ ቢሆንም እነዚህን የወሊድ መቆጣጠሪያዎች መካንነትን እንደማያስከትሉ ሊያውቁት የሚገባ እውነታ ነው፡፡

10) ኮንዶምን በሌሎች ቁሳቁሶች መተካት ይቻላል?

በፍፁም አይቻልም! በግብረ ሥጋ ግንኙነት ጊዜ ኮንዶምን በሌሎች እንደ ላስቲክ፣ ፈኛ፣እና የመሳሰሉ ቁሳቁሶች ተክቶ መጠቀም በፍፁም ተገቢ ያልሆነ ድርጊት እና ከአልተፈለገ እርግዝናም ሆነ ከአባላዘር በሽታም በጭራሽ እንደማይከላከል ሊያውቁት ይገባል፡፡

እባክዎን ለወዳጅዎ ያካፍሉ!

ጤና ይስጥልኝ

The post Health: ስለ እርግዝና መከላከያዎች 10 ነጥቦች appeared first on Zehabesha Amharic.

Viewing all 15006 articles
Browse latest View live