Quantcast
Channel: Ethiopian News | ዘ-ሐበሻ | Latest News Provider | News For All
Viewing all 15006 articles
Browse latest View live

ስለ ዳግማዊ ምንሊክ የ”ኒዎርክ ታይምስ ጋዜጣ”ያወጣው ጽሁፍ

$
0
0

ጋዜጣ (ኅዳር 7/1909 ዓም እ ኤ አቆጣጠር) የዛሬ 96 አመት የፃፈው ፅሁፍ ለአሁኑ ትውልድ ታሪካዊ ማስረጃ ነው

minilikኢትዮጵያ በየዘመኗ በሕልውናዋ ላይ የተቃጣባት የመበታተን አደጋን ያለፈችበት መንገድ የጦርነት መንገድ ብቻ አይደለም።ሆኖም ግን ከነበሩን የግጭት ታሪኮች በዘለለ በሕዝብ ዘንድ ተወዳጅ የነበሩ እና በሕዝብ ዘንድም የተወደዱ መሪዎች ነበሩን።ከእነኝህ ውስጥ ዳግማዊ ምንሊክ አንዱ ነበሩ። አፄ ምንሊክ ሀገር የማስተዳደር ጥበብን የተማሩት በአፄ ቴዎድሮስ እጅ ሆነው እድገታቸውን በንጉሡ ቤተመንግስት ማድረግ ከጀመሩበት ጊዜ ጀምሮ መሆኑን ብዙዎች ይስማማሉ።ንጉሡ የቀደሙ አባቶቻቸው አፄ ቴዎድሮስ እና አፄ ዮሐንስ ኢትዮጵያን አንድ የማድረግ አላማቸው እውን እንዲሆን ያደረጉ እድለኛ ንጉስም ናቸው።

አፄ ምንሊክ ኢትዮጵያን አንድ ከማድረግ አልፈው እስከ ኬንያ፣ሱዳን እና ሱማልያ ግዛት ድረስ ዘልቀው ገብተው በቅኝ ግዛት ይማቅቁ የነበሩ ህዝቦችን ነፃ ያወጣሉ የሚል ስጋት የነበረባቸው እና በወቅቱ በእነኚሁ የጎረቤት ሃገራት ላይ የጥቅም ፍላጎት የነበራቸው የአውሮፓ ሃገራት በብርቱ ተፈታትነዋቸው ነበር።በመሆኑም አዲስ የድንበር ውል ከኢትዮጵያ ጋር የመፈራረም ፍላጎት ከእንግሊዝ፣ፈረንሳይ እና ኢጣልያ በኩል ጥያቄ መነጻቱን የወቅቱ የታሪክ ድርሳናት ያወሳሉ።

ዛሬ ዛሬ በምንሊክ ላይ ታሪካዊ መሰረት የሌላቸው ቀድሞ አፄ ምንሊክ የቅኝ ግዛት ጥማታቸውን በገቱባቸው እና ቂም በያዙ ፀሐፊዎች የተፃፉ ናቸው ብለው ከሚነግሩን አስገራሚ ”የታሪክ” ፅሁፎች ውስጥ ”በምኒሊክ ዘመን እስከ አስር ሚልዮን ኦሮሞዎች አለቁ” የሚል ፅሁፍ በአንዳንድ የማህበራዊ ድህረ ገፆች ተለቀው ሲነበቡ መመልከት አስገራሚ የሰሞኑ ክስተት ነው።በፖለቲካው አለም በቂ ርዕዮተ አለምም ሆነ ፖለቲካዊ ፍልስፍና የጠፋባቸው አንዳንድ ወገኖች ”ትርፋማ” ብለው ያሰቡት የዘር ፖለቲካ በኢትዮጵያውያን መካከል መዝራት እና ከመቶ አመት በፊት የሆነውን የታሪክ ክስተት የአሁኑን ትውልድ በመውቀስ ትኩረት ለማግኘት ሲታትሩ መመልከት የዘመኑ አስቂኝ ተውኔት ነው።ዳግማዊ ምንሊክ ገና ብዙ የሚጠና ፖለቲካዊ፣ማኅበራዊ እና ወታደራዊ ክህሎት ባለቤት ለመሆናቸው በወቅቱ ከወጡት የዓለማችን ድንቅ ጋዜጦች አንዱ የ ኒውዮርክ ታይምስን እትም መመልከት ይበቃል።

ከእዚህ በታች በሚገኘው የኒውዮርክ ታይምስ ኅዳር 7/1909 ዓም እ ኤ አቆጣጠር እትም ላይ የኢትዮጵያ ጠቅላላ ሕዝብ ብዛትን 7,000,000 (ሰባት ሚልዮን) መሆኑን ያስቀምጣል። እዚህ ላይ አንዳንድ እራሳቸውን የታሪክ ምሁራን ነን በሚል ባልተጨበጠ ይልቁንም በምኒሊክ የቅኝ ግዛት ህልማቸው ከተደናቀፈባቸው ቂመኛ ፀሐፊዎች አነበብን የሚሉት እና የኦሮምኛ ተናጋሪ ኢትዮጵያውያንን ያማለሉ መስሏቸው ”ምንሊክ 10 ሚልዮን ኦሮሞ ገደሉ” እያሉ ኢትዮጵያ ከነበራት የህዝብ ብዛት (7 ሚልዮን) በላይ ቁጥር ሲጠሩ እፍረት አልተሰማቸውም።

”ማን ያውራ የነበረ” እንዲሉ የኒውዮርክ ታይምስ ጋዜጣ ኅዳር 7/1909 ዓም እ ኤ አቆጣጠር እትም ላይ ጋዜጣው አዲስ አበባ በነበረ በልዩ ዘጋቢው አማካይነት ስለንጉሡ እና ኢትዮጵያ ፖለቲካዊ እና ምጣኔ ሃብታዊ ሁኔታ ፅፎ ነበር።ጋዜጣው አፄ ምንሊክ እና አስተዳደራቸውን ከገለፀበት አረፍተ ነገር ውስጥ እነኝህ ይጠቀሳሉ –

– ኢትዮጵያን ወደ ህገመንግስታዊ የንጉሥ አስተዳደር ለመቀየር ሂደት ላይ መሆኗን፣

– የኢትዮጵያ ህዝብ ብዛት 7 ሚልዮን መሆኑን፣

– አፄ ምንሊክ ንጉሰ ነገስት ሲሆኑ ጦርነት የነበረው የአፄ ዮሐንስ ተተኪ እሳቸው መሆናቸውን ካልተቀበሉት ጋር ብቻ እንደ ነበር፣

– የአውሮፓውያንን ስልጣኔ ወደሀገራቸው ለማምጣት የባርያ ንግድን ከመዋጋታቸውም በላይ ነፃ ትምህርት ዕድል ዜጎች እንዲያገኙ መሰረት መጣላቸውን፣

– ምንሊክ እራሱ ልዩ ችሎታ ያላቸው ሰው መሆናቸውን። ከችሎታዎቻቸው መካከል ዲፕሎማት፣የፋይናንስ ባለሙያ እና ወታደር የሚሉት እንደሚጠቀሱ እና

– እንደ ዲፕሎማት እና ወታደር የጣልያንን ወረራ ኢትዮጵያ እንድታሸንፍ ያደረጉበት ጥበብ መሆኑን፣

የሚሉ ይገኙበታል።የጋዜጣውን ሙሉ ፅሁፍ ከእዚህ በታች ያለውን ሊንክ ከፍተው ያንብቡ።

የኒውዮርክ ታይምስ ጋዜጣ ኅዳር 7/1909 ዓም እ ኤ አቆጣጠር እትም ለማንበብ ይህንን ሊንክ ይክፈቱ።

Published: November 7, 1909 Copyright © The New York Times
http://query.nytimes.com/mem/archive-free/pdfres=F50A12F63A5A15738DDDAE0894D9415B898CF1D3

The post ስለ ዳግማዊ ምንሊክ የ” ኒዎርክ ታይምስ ጋዜጣ” ያወጣው ጽሁፍ appeared first on Zehabesha Amharic.


Health: ደም ማነስ! (የቀይ ደም ህዋሳት ለቅሶ)

$
0
0

ደም /Blood/    

የሰው ልጅ ከተለገሰው ስጦታ አንዱና ዋነኛው ደሙ ነው፡፡ ከሙቅ የቀጠነው፣ ከውሃ የወፈረው ደማችንን ወገቡ ላይ ብንከፍለው ሁለት ዓበይት ቡድኖች ይፈለፈላሉ፡፡ እነዚህም ፈሳሽ ክፍሉና ህዋስ ክፍሉ ናቸው፡፡ 55% እና 45% እንደየቅደም ተከተላቸው ይይዛሉ፡፡

ፈሳሽ ክፍሉ የተለያዩ ኤሌክትሮላይቶችን ለምሳሌ ሶዲየም፣ ፖታሲየም፣ ክሎሪን ወዘተ ፕሮቲኖችን ኢንዛይሞችን የመሳሰሉትን ሲይዝ የህዋስ ክፍሉ ደግሞ ሶስት አይነት ህዋሳትን ይይዛሉ፡፡ እነዚህም፡-
low blood pressue
1. ቀይ ደም ሕዋሳት /Red blood cells/

2. ነጭ የደም ሕዋሳት /White blood cells/

3. ፕላቶሌቶች /Platlets/ ናቸው፡፡

ድርሻቸውን ብንመለከት በአንድ ማይክሮ ሊትር ደም ውስጥ (የአንድ ሊትር አንድ ሚሊዮንኛ እንደማለት ነው) ከ4-6 ሚሊዮን የሚቆጠሩ ቀይ የደም ህዋሶች፣ ከ4,000-10,000-450,000 የሚቆጠሩ ፕላትሌቶችን ይይዛል፡፡

በአጠቃላይ ሰውነታችን ከተሰራበት 100 ትሪሊዮን ሴሎች ውስጥ 25 ትሪሊዮን ቀይ የደም ህዋሳት ናቸው፡፡ ስለዚህ ደም ማነስ ሲባል በደምሳሳው ይሄ ቀይ ሆኖ የምናየው የደማችን ማነስ ሳይሆን የቀይ ደም ህዋሳት ቁጥር መመናመንን ያመለክታል፡፡ ሌሎቹ ግን ሰላም ሊሆኑ ይችላሉ፡፡ ስለዚህ ምንም እንኳን የደም ማነስ ቢኖርም ነጭ የደም ህዋሳት የመከላከል ስራቸውን ይቀጥላሉ፣ ፕላትሌቶች ደግሞ የደም መፍሰስ እንዳይኖር ደምን በማርጋት ስራቸው ይወጠራሉ፡፡

– የደም ህዋሳትን ለማዘጋጀት የሚያስፈልጉ ጥሬ ዕቃዎችና ቅድመ ሁኔታዎች

1. ጤነኛ የሆነ መቅን /Healthly bone marrow/

ጤነኛ የቀይ ደም ህዋሳትን የሚያመርተው መቅን ከተለያዩ እክሎች የፀዳ መሆን አለበት፡፡ ለምሳሌ የመቅን ስንፈት /Boon marrow Aplasia/ ወይም መቅኑ በሌላ ጎጂ ህዋስ ከተወረረ ለምሳሌ በደም ካንሰር ህዋሳት ከተወረረ እንደ ጥንቱ በሰላም የማምረቱ ጉዳይ ጥያቄ ውስጥ ይገባል፡፡

2. ጤነኛ የሆነ ኩላሊት

ኩላሊትን የአጥንታችን መቅን ቀይ የደም ህዋሳትን እንዲያመርት ትዕዛዝ በመስጠቱ ረገድ ከ90% በላይ ስልጣን ተሰጥቷታል፡፡ ይህን ዓላማዋን ኢሪትሮፓዮቲን በተሰኘው የፕሮቲን አይነት ትፈፅማዋለች፡፡ ኩላሊት ላይ ችግር ካለ ይህም ፕሮቲን አብሮ ችግር ውስጥ ይገባል፡፡ ስለዚህ ስር የሰደደ የኩላሊት በሽተኞች ለደም ማነስ ችግር የሚጋለጡት ከዚህ የተነሳ ነው፡፡

3. በቂ የሆነ ፎሊክ አሲድና ቫይታሚን B12

እነዚህ የምግብ አይነቶች ለቀይ ደም ህዋሳት ቶሎ በስሎ መውጣት ወሳኝ ሚና ይጫወታሉ፡፡ እነሱም ከሌሉ በአጥንት መቅን ውስጥ የሚኖረው የቀይ ደም ህዋሳት እርባታ ፍጥነቱ ይዘገያል፡፡ ይሄን ለማካካስ እያንዳንዱ ህዋስ በግሉ ያብጣል፡፡ እውነተኛ ቅርፃቸውን ያጣሉ፡፡ ቶሎ ህዋሱ ፈንድቶ እንዲሞት በማድረግ ሰውዬውን ለደም ማነስ ሊያጋልጡ ይችላሉ፡፡

4. በቂ የሆነ የብረት ማዕድን

ሰውነታችን ብረትን እጅጉን አጥብቆ ይፈልገዋል፡፡ የሚፈልገው ደግሞ ባሌስትራ ለመስራት ሳይሆን የቀይ ደም ህዋሳትን ለመቀሸር ነው፡፡ የቀይ ደም ህዋሳትን የኦክስጅን ማኅፀን ያደረጋቸው ሔሞግሎቢን የተሰኘው ንጥረ ነገር ነው፡፡ ሄሞግሎቢን ደግሞ ማነው ብለን ብንጠይቅ የፕሮቲን የፓይሮልና የብረት ውህደት ነው፡፡ በሰውነታችን ውስጥ አለ ተብሎ ከሚታመነው ከ4-5 ግራም የሚደርሰው የብረት መጠን 65 ፐርሰንቱ የተከማቸው ቀይ ደም ህዋሳት ውስጥ ነው፡፡ ሳንባ ጋር የደረሰው ኦክስጅን በቀጥታ የሚያያዘው ሔሞግሎቢን ውስጥ ካለው የብረት አተም ጋር ነው፡፡ ስለዚህ ይህ ብረት የኦክስጅንን እጅ ይዞ ከእያንዳንዱ የሰውነታችን ህዋሳት ጋር በሰላም ያደርሰዋል፡፡ ደምን ያከበረው ትልቁ ጉዳይ እስትንፋሳችንን ማጓጓዙ ነው፡፡ ኦክስጅንን የማይሸከም ደም ካለ ገደል መግባት ይችላል፡፡ ይሄንን ስል ደም ኦክስጅንን ከመጠግረር ውጪ ሌላ ስራ የለውም ማለቴ አይደለም፡፡ ነገር ግን የሰውነታችን ህዋሳት አፍንና አፍንጫን አፍኖ ሌላን ስራ መስራት በአንድ እጅ ማጨብጨብ ስለሆነ ነው፡፡ ስለዚህ ብረት አጠረን ማለት ኦክስጅን አጠረን ማለት ነው፡፡ በአማካኝ በ100 ሚሊ ሊትር ቀይ ደም ህዋሳት ውስጥ 15 ግራም የሚደርስ ሔሞግሎቢን በወንዶች ሲኖር፤ በሴቶች ደግሞ 14 ግራም ይደርሳል፡፡ እያንዳንዱ ግራም ሔሞግሎቢን 1.34 ሚሊ ሊትር ኦክስጅንን ይሸከማል፡፡ ጠቅለል አድርገን ብናሰላው 100 ሚሊ ሊትር ቀይ ደም ሀዋሳት 20 ሚሊ ሊትር ኦክስጅን በወንዶች፣ 19 ሚሊ ሊትር ኦክስጅን በሴቶች ይዞ ይዞራል ማለት ነው፡፡ በዚሁ አጋጣሚ የአንዱ ጎልማሳ የደም መጠን ከ5-6 ሊትር ይደርሳል፡፡

5. ጤነኛ የሆነ ዘረመል

የደም ማነስ መንስኤዎች፡-

ከአንድ ህመምተኛ ደም ማነስን መርምሮ ማግኘት ጀግና ተብዬ የአንበሳ ቆዳ ካለበስኩ አያስብልም፡፡ ዋናው ጥያቄ ለምን ደሙ አነሰ ነው፡፡ ለምሳሌ እያለቀሰ ያለን ሰውዬ ተከፍቶ ነው የሚያለቅሰው ብሎ መናገር ነቢይ አያሰኝም፡፡ ይልቁንም ጥያቄው ለምን ተከፋ ነው፡፡ ሰው ሞቶበት ነው? ፍሬንዱ ዳምፕ አድርጋው ነው? አርሰናል ተሸንፎ? ወዘተ… የሚለውን ጥያቄ መለየቱ ነው መፍትሄ የሚያመጣው፡፡ ደም ማነስ የቀይ ደም ህዋሳት ለቅሶ ነው፡፡ ለምን አለቀሱ? ለደም ማነስ ድንኳን ተክለናል ያሉ የደም ምሁራን /Hematologists/ ብዙ ምክንያቶችን አንብተዋል፡፡ እነዚህም የሚከተሉት ናቸው፡፡

1. የቀይ ደም ህዋሳት ምርት መቀነስ

ይህ አይነቱ ምክንያት የሚከሰተው የሚመረቱት የቀይ ደም ህዋሳት ቁጥር ከሚሞቱት የቀይ ደም ህዋሳት በታች ሲሆን ነው፡፡ ከዚህ በታች የተዘረዘሩት እንደ መንስኤነት ሊወቀሱ ይችላሉ፡፡

– የብረት፣ ፎሊክ አሲድና ቫይታሚን B12  እጥረት

– የአጥንት መቅን ችግር

ይሄ ደግሞ ዋናው አምራቹ ክፍል ሲታመም ነው፡፡ ለምሳሌ በካንሰር ህዋሳት ሲወረር፣ እንዲሁም እሱን ሊጎዱ የሚችሉ አንዳድ መድሃኒቶች፣ ጨረሮች ወዘተ…

– የቀይ ደም ህዋሳት እንዲመረቱ የሚያበረታቱ ሆርሞኖች እጥረት ለምሳሌ፡- አነስተኛ የሆነ የታይሮይድ ሆርሞን፣ ስር የሰደደ የኩላሊት በሽታ፤

– ስር የሰደዱ  በሽታዎች ለምሳሌ ካንሰር፣ ቲቢ

2. የቀይ ደም ህዋሳት ጥፋት መጨመር

ጤነኛ በሆነ ሰውነት የቀይ ደም ህዋሳት በህይወት የሚቆዩት ለ120 ቀናት ነው፡፡ የቀይ ደም ህዋሳት ጥፋት መጨመር ማለት በሰውነታችን ውስጥ ከ100 ቀናት በታች ሲኖሩ ነው፡፡ የሆነ ሰው በወጣትነቱ ዕድሜ ቢሞት በአጭሩ ተቀጨ እንደምንለው እነዚህም ህዋሳት ኦክስጅንን በሚገባ ተሸክመው ሳይጠግቡ በአጭሩ ይቀጫሉ፡፡ ብዙ ምክንያቶች አሉ፡፡ ለምሳሌ የወባ በሽታ እንዲህ ሊያደርግ ይችላል፡፡ ሾተላይም ሽሉን ወይም ህፃኑን የሚገለው በዚህ መልኩ ነው፡፡

3. የደም መፍሰስ

ይህ አይነቱ የደም ማነስ የሚከሰተው ከሰውነታችን ያለ አግባብ በሚያመልጥ የደም መፍሰስ ምክንያት ነው፡፡ እነዚህ የደም መፍሰሶች ምንጫቸው የተለያየ ሊሆን ይችላል፡፡

– ከመጠን በላይ የሆነ የወር አበባ (በአንድ ዑደት ከ80 ሚሊ ሊትር በላይ ወይም ከ7 ቀን በላይ የሚፈሳት ከሆነ)

– ከጨጓራና አንጀት በሽታ የተነሳ የሚፈጠሩ መድማቶች

– በወሊድ፣ በውርጃ፣ በአደጋ ምክንያት የሚፈጠር መድማት

– አንዳንድ ጥገኛ ህዋሳት ለምሳሌ ቅድም ያየነው የደም ማነስ በሽተኛ የነበረበት የመንጠቆ ትል ለዚህ ማስረጃ ሊጠቀስ ይችላል፡፡ አንድ የመንጠቆ ትል በቀን 0.3-0.5 ሚሊ ሊትር ደም ከአንጀት ላይ ሊጠባ ይችላል፡፡ እንግዲህ አስቡት! በቀላሉ እንኳን ለሁለት ዓመት ከመንጠቆ ትሎች ጋር አብሮ የኖረ ሰው ደም ማነስ ቢይዘው ከብቶቹንም ጥሎ ሆስፒታል ቢመጣ የሚገርም አይሆንም፡፡

የደም ማነስ ምልክቶች

የደም ማነስ ምልክቶች የሚወሰኑት በሽተኛው ላይ በተከሰተበት ፍጥነት፣ መጠንና ደም ማነሱ ያመጣው መንስኤ አማካኝነት ነው፡፡ አንዳንዱ ህመምተኛ የደም ማነሱ አነስተኛ ከሆነ ምንም ላይሰማው ይችላል፡፡ የደም ማነሱ ከፍተኛ ከሆነ ግን እሱን ተከትሎ የሚመጡ ብዙ ምልክቶች ይኖራሉ፡፡

ድካም፣ ራስ ምታት፣ ማዞር፣ ድቀት፣ ለስራ በሚንቀሳቀስበት ጊዜ የአየር ማጠር ወይም ቁና ቁማ መተንፈስ፣ የራስን የልብ ምት ማድመጥ የተለመዱት የደም ማነስ ምልክቶች ናቸው፡፡ በተለይ የቀደመ የልብ በሽተኞች የሆኑ ሰዎች ለደም ማነስ በሚጋለጡበት ጊዜ የተፈጠረውን የኦክስጅን እጥረት ለመቅረፍ ብላ ልብ ከመጠን በላይ ስለምትሰራ ምልክቶቹ የገዘፉ ሊሆኑ ይችላሉ፡፡ ሌሎችም እንደ ደም ማነሱ አይነት ተያያዥ ምልክቶች ደም ማነሱን ሊያጅቡት ይችላሉ፡፡

ምን እናድርግ?

- አመጋገባችንን በተመለከተ

1. በብረት (Iron) የበለፀጉ ምግቦች መመገብ 

ከዓለም ህዝብ 30% የሚሆነው በደም ማነስ ተጠቅቷል፡፡ ከዚሁ ውስጥ ግማሽ ያህሉ የብረት እጥረት ነው የተጫወተበት፡፡ ከላይ እንደተገለፀው ሔሞግሎቢን የተሰኘው የቀይ ደም ህዋሳት ክፍል የተሰራበት ንጥረ ነገር አንዱ ብረት ነው፡፡ ደማችን በዚህ ምክንያት ቀይ ሆኗል፡፡ ለምሳሌ ኮፕር(መዳብ) ይህን ቦታ በሚሸፍንላቸው እንደነሎብስተር አይነት አሳዎች ደማቸው ሰማያዊ ሆኗል፡፡ ስለዚህ የብረት ማዕድን የበዛባቸው ምግቦችን መመገብ ደምን ቀይ ለማድረግ ብቻ ሳይሆን ቁጥራቸውንም ደህና አድርጎ ይሰቅልልናል፡፡ እነማናቸው ካላችሁ ቀይ ሥጋ፣ ጉበት፣ የዕንቁላል አስኳል፣ ሽንብራ፣ ባቄላ መብላት ይችላሉ፡፡

2. በፎሊክ አሲድና በቫይታሚን B12 የከበሩ ምግቦች መመገብ

ለሰውነታችን በቀን የሚያስፈልገው የፎሊክ አሲድ መጠን ከ0.4 ሚ.ግ አይበልጥም፡፡ ታዲያ 100 ግራ የሚመዝን ቅጠላ ቅጠል የተመገበ ሰው ከ1 ሚ.ግ የበለጠ ፎሊክ አሲድ ማግኘት ይችላል፡፡ ጠቅላላ የሰውነታችን የፎሊክ አሲድ ጎተራ 5 ሚ.ግ ነው፡፡ ታዲያ አነስተኛ የሆነ ፎሊክ አሲድ በየቀኑ የሚመገብ ሰው ካለ በ4 ወር ውስጥ የደም ማነስ ተጠቂ ሊሆን ይችላል፡፡ ስለዚህ ለምን ጠላት ደስ ይበለው? ቆስጣ፣ ሰላጣ፣ ባቄላ፣ ሎሚ፣ ብርቱካን፣ ሃብሃብ፣ ጉበት፣ ኩላሊት፣ እንጉዳይ እንክት አድርገው ቢበሉ በዚህ ምክንያት የሚመጣ የደም ማነስን አስቀሩ ማለት ነው፡፡

ቫይታሚን B12ን ቢሆን ሰውነታችን እንዲሁ ይፈልገዋል፡፡ ከፎሊክ አሲድ የሚለየው የሚያስፈልገን የቀን ቀለብ ከፎሌት የሚያንስ በመሆኑ ብዙ እንኳን ባንመገብ ደም ማነሱ ሊከሰትብን የሚችለው ከ3-5 ዓመታት ባሉት ጊዜ ውስጥ ነው፡፡ ሌላው ቁም ነገር ደግሞ ቫይታሚን B12 ከእፅዋት እናገኘዋለን፡፡ ስለዚህ ከስጋ ተዋፅኦዎች ከዓሣና ከወተት ውጤቶች ላይ መፈለግ ግድ ነው፡፡

– ስር ለሰደዱ በሽታዎች መፍትሄ መፈለግ

ለምሳሌ የቲቢ በሽታ ከሆነ ቶሎ መታከም፡፡ የደም ካንሰርም ከሆነ በተለይ ልጆች ላይ አመርቂ የሆነ ውጤት ስላለው በጊዜው መፍትሄ መፈለግ ደም ማነሱንም ሆነ ዋናውን በሽታ ቶሎ ማስወገድ ይቻላል፡፡

– የሚሰጠንን የደም ማነስ መድሃኒቶች በአግባቡ መውሰድ

በተለይ ከፍተኛ የሆነ የብረት፣ የፎሊክ አሲድና ቫይታሚን B12 ፍላጎት የሚንርበት የእርግዝና ወቅት ላይ የሚሰጥ መድሃኒት አለ፡፡ መድሃኒቱ ትንሽ ጨጓራን የመንካት ጠባይ ስላለው፣ በተጨማሪም ዘለግ ላለ ጊዜ ስለሚወሰድ ለምሳሌ ለሶስት ወር ያህል ተጠቃሚው መድሃኒቱን የማቋረጥ ነገር ይታይበታል፡፡ ነገር ግን ለጨጓራው ከሐኪም ሌላ መፍትሄ መፈለግ ይሻላል እንጂ መድሃኒቱን ባያቋርጡት መልካም ነው፡፡

ደም

ለሰው መድሃኒቱ ሰው ነው እንደሚባለው ሁሉ ለደም ማነስም መድሃኒቱ ደም የሚሆንበት ጊዜ አለ፡፡ ለምሳሌ ብዙ ደም ፈሶት ሔሞግሎቢኑ በጣም የወረደ ሰው ጉበት ብላና ዳን ማለት እኔ የምሞተው ዛሬ ማታ ላሜ የምትወልደው ለፍልሰታ እንዳለችው ሴት ነው የሚሆነው፡፡ ምክንያቱም በእንደዚህ አይነት ሁኔታ የፈሰሰ ደም ቶሎ መተካት ስላለበት ጉበቱን ለጊዜው ፍሪጅ ውስጥ ማስቀመጥ ይሻላል፡፡ ይልቁንም የሚመሳሰለውን ደም ፈልጎ መለገስ ህመምተኛውን ከሞት በእጅጉ ይታደገዋል፡፡

- ከኢንፌክሽንና ከአንዳንድ ጥገኛ ራስን መጠበቅ 

ለምሳሌ ወባ ደምን ከማሳነስ ጀምሮ እስከ መግደል ታደርሳለች፡፡ ስለዚህ ራስን ከወባ ትንኝ መጠበቅ ብልህነት ነው፡፡ የራስን የግል ንፅህና  መጠበቅም ቅድም መግቢያችን ላይ እንዳየነው ህመምተኛ በጥገኛ ህዋሳት ከመጠቃት ያርቃል፡፡

መቅንን መተካት

ይህ አይነቱ ህክምና የመቅን ስንፈተ ስጋ ጠማቸው ህመምተኞች የሚከናወንና እጅግ ውስብስብ ቴክኖሎጂን የሚፈልግ ነው፡፡

መልካም ጊዜ፡፡

The post Health: ደም ማነስ! (የቀይ ደም ህዋሳት ለቅሶ) appeared first on Zehabesha Amharic.

አባይ ጸሐዬ በኦሮሞ ሕዝብ ላይ የዛቱበት ድምጽ ተለቀቀ –“በአ.አ. ማስተር ፕላን ላይ ዳግም ጥያቄ ካነሱ ልክ እናስገባቸዋለን”አሉ

$
0
0

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያንን ም እመናንን ለሁለት በመክፈል የኢሕአዴግን የስልጣን ዘመን ያረዘሙት ሕወሓቱ አባይ ጸሃዬ ሰሞኑን በኦሮሞ ሕዝብ ላይ ዛቱ:: ድምጻቸው ተቀርጾም በኦሮሚያ ሚዲያ ኔትወርክ በኩል ለሕዝብ ይፋ ሆነ:: አባይ ጸሓዬ የአዲስ አበባ ማስተር ፕላንን ጉዳይ እንዲራዘም የተደረገው ሕዝቡ ባነሳው ተቃውሞ እንዳልሆነ ገልጸው በቅርቡ ተግባራዊ እንደሚሆን ገልጸዋል::

የአዲስ አበባ ማስተር ፕላን እንዳይሳካ የኦህዴድ ባለስልጣናትም ተባብረዋል ያሉት አባይ ጸሓዬ በአዲስ አበባ ማስተር ፕላን ማስፋፊያ ዙሪያ ዳግመኛ ጥያቄ የሚያነሱትን ልክ እናስገባቸዋለን ብለዋል::

ከኦሮሚያ ሚድያ ኔትወርክ የተገኘው ዜና የሚከተለው ነው::

አቶ አባይ ጸሐዬ

አቶ አባይ ጸሐዬ

The post አባይ ጸሐዬ በኦሮሞ ሕዝብ ላይ የዛቱበት ድምጽ ተለቀቀ – “በአ.አ. ማስተር ፕላን ላይ ዳግም ጥያቄ ካነሱ ልክ እናስገባቸዋለን” አሉ appeared first on Zehabesha Amharic.

እናንተ ለአገልግሎት ነበር። እነሱ ዘበኛ ነው የሚፈልጉት። –ዳዊት ዳባ

$
0
0

እርጉዝ ነኝ እያለችህ ሴትን ልጅ ሆዷን ረግጠህ ፅንስ አስወረድክ። አሮጊትና ሽማግሌ በጫማ ጥፊ ሳይቀር የሚደበድቡ  አሉ።  አንድን ሚስኪን ወገን አስርና አስራ አምስት ሆነው ለጉድ ሲቀጠቅጡም በተደጋጋሚ አየን። መፍክር ብቻ በጁ ይዞ የጋራ ለሆነ መብትና በደል  ሊያሰማ አደባባይ የወጣ ዜጋ  አቅማቸውን ለማሳየት በብዙ ቁጥር ደግሞ ስልጠናችውን የጠቀማሉ። የማጥቂያ እቅድ ይሰጣቸዋል። ቆረጣው፤ ከብባአድርገው፤ አደፍጠው ብቻ ያለ ወታደራዊ እውቀት ሁሉ ተፈፃሚ ማድረጉ እንዳቅሚቲ  አይቀራቸውም ። ይህ ሁሉ መሀል ከተማ  አዲስ አበባ ውስጥም ነው እየተፈፀመ ያለው። በዚህ ሰሞን እንደገና አገረሸ እንጂ ይህን አይነቱ ታሪክ ሀያ አራት አመት አለው። ብዙ ንፅሁን ዜጎች መገደላቸውን፤ አካለ ጎዶሎ መሆናቸውንና ስብእናቸው መደፈሩ ተመዝግቧል። ሁላችንም ሳንሰማው ያልቀረነው። በአገር አይቻል ሆኖ ለሰው ልጅ ሂወት ክብር በሚሰጡ በሌሎች አገሮች ፍርድ ቤት እየታየ ያለውና  በአለማቀፍ ፍርድ ቤት  ተራ እየጠበቁ ያሉ ዘር ማጥፋት፤ ዘር ማፅዳት፤ በንፅሀን ላይ የተፈፀመ ፍጅት የመሳሰሉ ከባባድ ኢትዬጵያዊ ክሶች ገዥዎቻችን  ስማቸው ተጠርቶ ቢከሰሱበትም  እነሱ ወርደው ተኩሰው ስለገደሉ እንዳልሆነ  ግልፅ ነው።

ለተቀደሰ አገራዊ  ተግባር፤ የሂወት መሰዋትነት ድረስ የሚሻ ግልጋሎት ለመስጠት የፈቀዳችሁ ብዙ መቶ ሺዎች ናችሁ። በቀጥታ የዚህ አይነት ወንጀሎች ላይ ድርሻ ያላቸውን ከውስጣችሁ ማጥራትና ማወቅ ቢቻል ቁጥራቸው እጅግ ጥቂት ሊሆኑ ይችላል ይባል። ከዚህም አልፎ ከውስጣችሁ በዘር ወይ በፖለቲካ አመለካከት ተመርጦ ተመሳሳይ ለሆኑ የሰራዊቱ አባላት ግድጅ የሚሰጥበትና ወንጀሉ የሚፈፀምበት ሁኔታም መኖሩ አይቀርም። እውነታው ይህ  ቢሆን እንኳ ለጥቃቱ ሰላበዎች ሆነ ለጠቅላላው ዜጋ በዚህ ደረጃ አስፍቶና በትኖ የማየት ግዴታ ግን  የለበትም። እውነት ለመናገርም መረጃውም የለውም።  የሚያውቀው ከወንጀሉ ስፋት፤ ለረጅም ጊዜ የቀጠለ መሆኑንና ከተጎጂዎች ብዛት አኳያ  ቀላል የማይባል ቁጥር የላቸው ጓዶቻችሁ ድርሻ እያደረጉበት እንዳለ ነው። በዚህ እናንተም ብትሆኑ የምትስማሙበት ነው።

አዎ ዜጋው የሚረዳውም ሆነ የሚያውቀው  ሰራዊትነቱን፤ ፖሊስነቱን  ዩኒፎርሙን በአጠቃላይ ሞያው   የጋራ መለያችሁ መሆኑን  ነው።  ግን ለምን? ለሚለው ጥያቆም ሆነ ወንጀለኞቹ ጣሰው ይሁን መገርሳ ወይ ገብሬ የሚያውቀው ነገር የለም።  እናንተ ግን ታውቋችዋላችሁ። ስለዚህም በስልጠና በማደንዘዝም ይሁን በማስፈራራት ወገናዊነቱን ጨርሰው ክውስጣችሁ ካልሟጠጡት አንድ ነገር ማድርግያው ጊዜው አሁን ነው። ለወገን ፤ ለእውነት፤ አቅም ለሌው የመቆሙ ስብእና ከሌለ እንኳ ቅንጣት ታክል ለራሳችሁ የምትሰጡት ክብር ካል እባካችሁ ይህ  ፍፁም ሰላማዊና ንፁሀን የሆኑ ወገናችሁን፤  ህፃን፤ ሴት፤ አሮጊት  ሳይለይ  የተያያዙት ፍጅት ይብቃ ይባል። ዋጋም ቢያስከፍልም  በኛ ስም አይደረግ ወይ አናደርግም  ማለት የግድም የቶሎም ሆኗል።  አሳሳቢ ያደረገው ይህ ፍጅት በመላ አገሪቱ ለሀያ ሶስት አመት የቀጠለ መሆኑ ብቻ ሳይሆን ከጊዜ ግዜ እየጨመረና ዘግናኝ እየሆነ መሄዱም ነው።

ለመሆኑ ማን ነህ አንተ?። ማን ናችሁ?።  ይህን ደጋግሞ መጠየቅና ማስታወስ የግዜው አንገብጋቢ ቁምነገር ሆኗል። ብዙ ብዥታ ውስጥ ያሉ አሉና። ሁላችሁም ሊሰኝ በሚችል ዝቅተኛ ኑሮ ካለው ቤተሰብ እንደውም እንደኔ ከደሀ ቤተሰብ የመጣችሁ ናችሁ። አብዛኛዎቻችሁ ፍዳ እያየ ያለው የገበሬ ልጆች ናችሁ። ገዳዬቹም ቢሆኑ ይህ ውሸት ነው መቼም አይሉም። ካሉ ግን ከትላልቆቹ ባለስልጣናት ግዴለም ይቅር። ከሚታወቁ ከመለስተኛ ባለስልጣናትና ከባለ ጊዜዎች አብረዋችሁ የሚያገለግሉ አስር የሰራዊት አባላትን  ቁጠሩ እስቲ?። እሺ አምስት።  ከሶስት መቶ ሺ ከሚጠጋ ብዛት  በእርግጠኛነት ለስም አንድ እንኳ እንትና ማለት አይቻልም። የለማ። መራርም ቢሆን እውነታው ሁላችሁም ከሚገደለው፤ ከሚደበደበው፤ ከሚዋረደውና ነፃነቱን ከተቀማው ወገን ናችሁ። ቪላ ውስጥ አትኖሩም። በመኪና ሽር ነው እንዴ የምትሉት። የሚከራይ ሀንፃ ባለቤት ናችሁ። የፋብሪካስ ወይ የባንክ ሼር ሆልደርስ። ነው ያስመጪና ላኪ ንግድ እያጧጧፋችሁ ነው። መልሱዋ።

በግልፅ መቀመጥም ያለበት  ሁሌም ወታደራዊ ስልጠና ስትወሰዱ በተወሰነ ደረጃ ለትልቅ አገራዊ ፋይዳ ሲባል ማንነታችሁን እንደ አዲስ ለመፍጠር ነው። ወይ እንደሚፈለገው ለመሞረድ፤ ለማስተካከል፤ ታዛዥና ጨከን ያላችሁ እንድትሆኑ ላመድረግ ነው። ይህ አዲስም አይደለም። የትም የሚሰራባት ነው። ለሁሌው በዋናነት  አላማው አገራችሁንና ወገናችሁን ከጥቃት በመከላከል ግልጋሎታችሁ ስኬታማ እንድትሆኑ ሰለሚጠቅም ታስቦበትና ታውቆ የሚደረግ ነው። የመከላከያ ሰራዊት፤ የፖሊስ ሰራዊት የተቀደሰና ክብር ያለው በምንም አይነት ወጋ ሊተመን የማይችል ከባድ የሆነ “ግልጋሎት” ያደረገውም ይህ ለሌሎች ሲባል  እራስን እንዳዲስ ለመቀረፅ ፍቃደኛ መሆንና የሂወት መሰዋትነት መክፈል ድረስ የሚሄድ አገልግሎት ያለበት መሆኑ ነው።

መጥፎነቱ  የአገር ሉአላዊነት ማስጠበቅና ወገንታዊነት ከውስጡ ሲወጣ  ዘበኝነት ሆኖ ቁጭ ይላል። አሁን  በአገራችን እንዳለው ማለት ነው። አላማው አንድና አንድ  ስልጣንና ባለስልጣን መጠበቅ ሲሆን። ባልስልጣናቱ እንደሁላችንም እንደናንተም ጭምር ሰውም  ዜጋም ናቸው አለቀ። የምትጠብቁት ለአገር አለን የሚሉትን  እርአይ፤ ሀሳብና አላማም ቢሆን እንኳ ያው ዘበኝነት ነው የሚሆነው። ለምን ለምትሉ ? መልካም የሆነ ሀሳብና እርአይ ኖሯቸው ሆኖ ቢሆን እንኳ እርአያቸው እናንተም ሌሎቻችንም ለአገራችንና ለህዘባችን ከለን እርአይና ሀሳብ ጋር ተወዳድሮ ማሸነፍ እንጂ መጠበቅም ዘበኛ ሊቆምለትም በጭራሽ አይገባም ነበር። ለነገሩ ነው እንጂ ካልተካካድን በሁኗ ኢትዬጵያችን እየተጠበቀ ያለው ከዚህም እጅጉኑ በጣም በጣም ይወርዳል። የገዢዎች  ምቾት፤ ጥቅም፤   ወንጀል፤ብልግና፤ጥጋብ የቀረውን  ጨምሩበት። ታዲያ  ይህ ዘበኝነት አይደለም የሚል ካለ ምን ሊባል ነው።  ዘበኝነት በሚያደርጉት በእነዚህ ምክንያቶች ላይ በያንዳንዳቸው ላይ ብዙ ማስረጃዎችን መደርደር ይቻላል። ላለማብዛት ሁላችንም የምናውቀውን አንድ እውነት ብቻ በበቂ ገላጭ ነው። ሁሉም ትናንት በነጠላ ጫማ መጥተው ዛሬ ምሳ አዲስ አበባ እራት ዱባይ የሚበሉ ሚሊዬነሮች ናቸው። የሆኑት ደግሞ ሰርቀው ነው።እንዳይጠየቁ ግርጋድ ሆናችሁ በየት በኩል።

ሌላው በግልፅ መታወቅ ያለበት ቅዱስ የሆነውን አገራዊ አገልግሎት ወደዘበኝነት የመቀየሩ ጥረትና ጉጉት የየትኛዎቹም አንባገነንች ሁሉ ወና ስራም የሁሌም ያላሰለሰ ጥረት መሆኑን ነው። ይህም እንግዳም አዲስም አይደለም። አንባገነኖች በነበሩበት ግዜ ሁሉ የተፈፀመና ታሪክ ጥርት አድርጎ በተደጋግሞ የመዘገበው እውነት ነው። ከአንባገነኖች በኩል ሆኖ “ግን ለምን?” ለሚለው ጥያቄ መልስ መስጠቱም እጅግ ቀላል ነው። ስልጣን ላይ የመዘባነኛው ጉልበት በነሱ እጅ እንዳልሆነ ስለሚያውቁ ነው። ባጭሩ ጉልበቱ በጁ የሆነው (ሰራዊቱ)  ሊጠብቃቸው ፍቃደኛ እስከሆነ ጊዜ ብቻ የስልጣን እድሜያቸው ቀጠይ መሆኑን አሳምረው ስለሚያውቁ ነው። በዚህ ጉዳይ ላይ ጥናት የአደረጉ ሁሉ የሚስማሙበትና አጥጋቢ መልስ ሊያገኙለት ስላልቻሉ  “ታልቅ  የሆነ እንቆቅልሽ” ብለው የሚደመድሙት መሳርያ በጁ ካለውና ጉልባትም ከሆነው ወገን ሆነው “ግን ለምን?” ለሚለው ጥያቄ አጥጋቢ መልስ ለመስጠት ሲሞከሩ ነው።

ቀጣይ ባይሆንም ያሁኖቹ የኛ አንባገነኖች ጥሩ ዘበኛ መፍጠሩ ላይ አብዝቶ ተሳክቶላቸውል።ተሳክቶላቸዋል የሚያሰኘው በመጀመርያ ሀያ አራት አመት ረጅም ጊዜ ነው።  በዛ ላይ በዚህ ረጅም ጊዜ ይህ ነው የሚባል እንቢተኛነትና ማንገራገር ሳይገጥማቸውና ሳይፈሩ መጠበቅ ስለቻሉም ነው። የአሁኑን የኛን በጣም አስገራሚና የበለጠ እንቆቅል የሚያደርገውም ጉዳይ ደግሞ አለ። ከመነሻው በአገር ፍቅርና በወገንታዊነት አልታሰራችሁም። ስለመብት፤ ስለአድሎ፤ ስለክብርና ስለምቾት ስለመሳሰሉት ተደርጎ እንዳይወሰድ በነዚህ ሁሉ ምክንያቶች ትግሉ ላይ ከመጀመርያው ረድፍ ላይ መቆም ይገባችሁ የነበራችሁ ናችሁ መሳርያ ይዛችሁ ሰጥ ለጥ ባለ ሁኔታ ዘበኝነትን ምርጫ ያደረጋችሁት።  እየሰነዘርኩ ያለሁት ወቀሳ ከባድም  በጅምላም ነው።ወግዱ ብለው የተገደሉና ዛሬም ድረስ ታስረው ፍዳ እያዩ ያሉ እንዳሉ ይታወቃል። ጥለው የወጡም ብዙ ናቸው። ይህ እየጣሉ መውጣቱ እራሱ እየበዛ መሄዱ ብቻ ሳይሆን  ዞሮ መውጋት ድረስ ሁሉ ሄዷል። ያም ሆኖ ወቀሳዬ አግባብ ያለውና ግልፅ ብሎ የሚታይ ጥቁር እውነታ ያለው ነዋ። ከውስጣችሁ ጥቂቶች ለነፃነት ሲሉ የወሰዷቸው እነዚህ እርምጃዎች የቀራችሁትን የሚያስከብርና የሚያስፈራ ገና በድንብ አልሆነም። ለዚህ ዛሬም ድረስ ተቀያይረው ይሆናል እንጂ ለሀያ አራት አመት  የሚያዟችሁ ተጋዳላይ የነበሩ ትግሬዎች መሆናቸውን  ማስታወሱ በቂ ነው።

ከላይ እነሱ የተንደላቀቁ ገዢዎች እናንተ በዘበኝነት ይህን አይነቱ ግንኙነት የግዜ ጉዳይ ነው አይቀጥልም ብያለው።  ለማቀሳሰር ግን በጭራሽ አይደለም። እንደእስከአሁኑ ግንኙነታችሁን በያዙበት መንገድ ለዛውም “አድሎ” ኖሮበት አይደለም መሳርያ በጁ ያለውን በማክበር፤ በጥቅማ ጥቅም በመደለልና  ሙጫ በመሆን  ተሞክሮም የተፋረሰ፤ የማይፀና የማያዛልቅ ግንኙነት እንደሆነ ተደጋግሞ የታየ ስለሆነና አሳምሬ ስለማውቅ ነው።   አስተውላችሁ ከሆነ ደግሞ ገዢዎቻችን በዚህ መንገድ መቀጠሉ አመፀኛውን እያሳደገ መሄዱ  ያሳስባቸው ስለጀመረ   የስትራተጂ ለውጥ አድርገዋል።  ይሄ አሁን የምታዩት የሰራዊት ቀን፤ ደርሶ አክባሪና ተቆርቋሪ ሆኖ መታየቱና የሞራል ግንባታው ሁሉ አላማው አንድና አንድ እራስችሁን ቻሉ እንዳይመጣ ነው። ይህን አይነቱ ነገር ገና እየጨመረ የሚሄድ ሆያ ሆዬ ነው። እመኑኝ ወደፊትም የማይፈጥሩት  የማይሞክሩት ነገር አይኖርም። እሹሩሩው ገና ላዛ ያጣል። ሰሞኑን በቴሌቪዥን አያየሁ ነው። ፈዳላ የኪነት ሰዎችና ተሰሚነት ያላቸው ዜጎች አፍ መጠቀም ሁሉ  ግድ ብሏል። እስከቦርጫቸው ቡሽ-አብ  ከናንተ ጋር እያስመቷቸው ነው አይደል?።

ለማንኛውም ያለመዋትነት የሚመጣ ነፃነት የለም የሚለው አባባል እውነት ነው። እኛ ግን መሰዋትነት እስከተከፈለ ድል የግድ ብለን እንነሳ።  ይህም ብቻ አይደለም መሰዋትነቱ እጅግ እጅግ በቀነሰ የሚለውም  መመርያችን መሆን አለበት። ከተናበብንና ከቀናጀነው ያለ መሰዋትነትም ነፃነታችንን ልናገኝ የምንችልበት ክፍተት አይታያችሁም።  ለኔ ይታየኛል። ድግሞም አለ።

ናፃ አውጪ ሆናችሁ ከዱር ላልመጣችሁ የሰራዊቱ አባላት በሙሉ።እንኳን ለአራተኛ አመት የሰራዊቱ ቀን በሰላምና በጤና አደረሳችሁ። አገልግሎቱ የተቀደሰ ነው። በመጀመርያ ሰራዊቱን ለተቀላቀላችሁበት አላማ ዜጎች ሁሉ ክብሩ አለን። የኛንና የናንተን ጉዳይ በዚህ ልዝጋው።

ስነሳ ለመፃፍ ያሰብኩት በቅርቡ  “እና አሁን ምንድን ነው መደረግ ያለበት” በሚል የፃፍኩት ፅሁፍ ላይ ቆያይቶ የታሰሰበኝን ይጠቅማል ወቅታዊም ነው ብዬ ስለሳበኩ እላዩ ላይ ለመጨመር ነበር። የእህታችን መደብደብና ልጇን ብግፍ ማጣቷን መስማቴ አስመመኝ እና ሳልወድ ሀሳቤ ከጥቃቱ ላይ መውረድ አልቻለም መሰለኝ ወደሰራዊቱ መንፈሴ ተሳበ። በተደጋጋሚ አርእስት መቀየር ነበረብኝ። ስብሰለሰልበት የነበረ ስለሆነ ግን ትንሽ የተነሳሁበት ላይ እላለው።

ተስማማን አልተሰማማን የዚህ ምርጫ ጠቅላላ ሂደቱ  ተቃውሞ፤ እንቢታ፤ ወግዱልንም ነው። ጥያቄው ሂደቱን ጉልበታም በሆነ በዚህኛው መንገድ በሚታይ መንገድ ልንጠቀመብት እንችላለን አንችልም? የሚለው ነው። ለማስኬድ የሚያስችለንን ዝግጅት ሰርተናል ወይ? አለን ወይ? የሚለው ነው።  ከምልከታም አኳያ ብንወስደው የዚህ ምርጫ ትግሉ ላይ ሊኖረው ሚችል ጠቀሜታ የምርጫ ካርድ መውሰድ። ከዛም ከመምረጥ። ድምፁ በአግባቡ ከመቆጠር፤ ከዛም የሸነፈ ስልጣን ይወስዳል ከሚለው አንድ አቅጣጫ ከሆነ ምልከታ ወጥተን ካየነው ብቻ ነው  ሊታየን የሚችለው። ይህም ሆኖ  የመጨረሻውን ውሳኔ አገር ውስጥ ላሉት ድርጅቶች መተው የብልህም አስተውሎትም ያለው ያደርገው ነበር። ሊተውላቸውም ይገባቸውም ነበር። እነሱ መታገሉ በቃን ይህ መንገድ አያዋጣም ሳይሉ የሌሎቻችን አቋም ሆነ ውሳኔ የሚጎዳው ወያኔን ሳይሆን በከፋ ሁኔታ ውስጥ እየጣሩ ያሉትን ነው። በእጅጉ ጥረታቸው ላይ ተእፅኖ አሳዳሪ ነው። ይህ ደግሞ የትኛውንም አይነት ትግል ቅንጣት ታክል አይበረታውም። ጉዳት እንጂ ግዚያዊም እንኳ ፖለቲካል ትርፍም የለውም።  መታወቅ ያለበት ህዝባዊ አንቢታ ዝም ብሎ አይወለድም። በዋናነት ማጫርያ፤ የብዙዎች ትኩረትና ከፍተኛ ደረጃ የሚገኝ ፖለቲካዊ የህዝብ ተሳትፎና ንቃት እንዲሁም በሀሳቡ ያበረና የተሳሰረ ህዝብ ይፈልጋል።

ምርጫ አለ ብሏል ከፈለገ  ሀሳባችንን ቀይረናል የለም ይበሉ። ወይ ሰማያዊ ፓርቲን ያግድ። በኛ በኩል እነሱ ከሚፈልጉትና ሊጫወቱት ከሚፈልጉት  ምርጫ ካርድ ከመያዝና ከዛም መርጦ አርፎ ከመቀመጥ የፈዛዛ ነገር ሂደቱን ልናተለቅው ግን ይገባል። አንድነቶች ሰማያዊ ፓርቲን እየተቀላቀሉ ነው።  ይህንን ሌሎቻችንም በገፍ ድርሻ አድርገንበትና  እናስፈው። እየተሰባሰብን ቀነ ቀጠሮ እያስያዝን ሰማያዊ ቢሮ በመሄድ ምን እናግዝ ማለቱ አንዱ መንገድ ነው። የከፍተኛ ደረጃ ተማሪዎች፤ ቤተሰቦቻቸው በወያኔ የተገደሉባቻውና የታሰሩባቸው ቤተሰቦች፤ ያለአግባብ ከስራ የተባረራችሁ ዜጎች፤ ቤታቸሁ የፈረሰና የተፈናቀላችሁ ዜጎች፤ ስራ አጦች፤የአገዛዙ በሀይማኖታቸረሁ ጣልቃ መግባቱ የስመረራችሁ ዜጎች፤ ሞያችሁን በነፃነት መተግበር የተቸገራችሁ ዜጎች። የህግ ሰዎች፤ መምህራን፤ ዶክተሮች። ለተለየ መብት ተቆርቋሪ ዜጎች። ሴቶች፤ ያካል ጉዳተኞች፤ በረንዳ ተዳዳሪዎች፤ ነዲያን። የመኖርያ ቤት ችግርተኞች። ውሀ እየጠፋ የምትቸገሩና መግዘት የመረራችሁ ዜጎች። ካስፈለገ ጄሪካል ይዛችሁ። በመብራት መጥፋት የተማረረችሁ ዜጎች።  በአጠቃላይ በዚህ ስርአት እየተጎዳ ያለው እንደው አገሬው ነው። በየምድብህ ተራ እየገባህ እየተሰባሰብክ ወደሰማያዊ ትመም። ሳትጠራ ላግዝ ብለህ። ቅስቀሳ ላይ ስብሰባ ላይ በሚሊዬኖች ተገኝ። ፖለቲካዊ አየሩን በመላ አገሪቱ በለውጥ ፈላጊው  ምኞትና ፍላጎት ሙላው። ሀሳባቸውን ከበህና አይለህበት መተንፈሻ አየር አሳጣው። እንደማንፈልጋቸው፤ እንዳልተመቹን ዛሬውኑ ግልፅ ይሁንላቸው።  ይህ አይነቱ ትግል ሰዎቻችንን ስለሚታወቁ ነው እንጂ ከደህንነት አኳአ እንከን የማይወጣለት ነው። ያም ሆኖ ያነሰ መሰዋትነት ያለው። ለጥቃት ይህን ያህል የማያጋልጥ። ቀላል፤ ሰላማዊ ከዛም በላይ ህጋዊም ለጊዜው የተፈቀደ ነው። ከተንጓተትን አናሳካውም መፍጠንና መረባረብን ይፈልጋል። አስጀማሪ ጀግኖችንም ይፈልጋል።

በውጪ ገና የትግል አይነት አፎካክረንና ትንታኔ ሰጥተን አልጨረስንም። እገዛችን ቢኖርም እንደተለመደው ዘግይቶ ምን አልባትም መታሰር ስትጀምሩ ወይ ሰረቁ ስንል ነው የሚደርሰው። ከአስር አመት በሗላም ይህው ለምን አልባቱ ትግሉን የሚያስቀጥል ያበረና ደርሶ ደግሞ የማይጨቃጨቅ አካል ማቆም አልሆነላቸውም። ቢያውቁበት ድሮ ዝግጅቱ አልቆ ሊኖር የሚችልን የገንዘብ ችግር ቀርፈው ነበር። ተሰሚነታቸው ጎልብቶ ተነስ፤ ትመም ተረባረብ ነበር መሆን ያለበት። ለማንኛውም ለሁላችንም በብዙ ቁጥር ትግሉ ላይ ፍቱን ነው። ከተቻለ በደሌ ቢራ ሳይሆን የኦሮሞ ህዝብ ሆይ ጊዜው አሁን ነበር።

 

2007 election

The post እናንተ ለአገልግሎት ነበር። እነሱ ዘበኛ ነው የሚፈልጉት። – ዳዊት ዳባ appeared first on Zehabesha Amharic.

ኦብኮ በገዥው ፓርቲ ወከባ እየደረሰብኝ ነው አለ

$
0
0

‹‹በጋራ ምክር ቤቱ እየተጠቀምን አይደለም›› አቶ ቶሎሳ ተስፋዬ የኦብኮ ሊቀመንበር

OFC_2009ኦብኮ ኢህአዴግን ጨምሮ ሰባት የፖለቲካ ፓርቲዎች የመሰረቱት የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት አባል ሆኖ እየተንቀሳቀሰ ቢሆንም የምክር ቤቱን ስምምነት በጣሰ መልኩ በአባላቱ ላይ ከፍተኛ ወከባ እየደረሰባቸው እንደሚገኝ እና የጋራ ምክር ቤቱም ህጎቹን ለማስከበር አቅም ማጣቱን የፓርቲው ሊቀመንበር አቶ ቶሎሳ ተስፋዬ ለነገረ ኢትዮጵያ ገለጸዋል፡፡ የኦህዴድ ካድሬዎች የኦብኮን አባላት በማስፈራራት፣ ቤተሰቦቻቸውን በማሸማቀቅና በማዋከብ ከምርጫ እጩነታቸው ራሳቸውን እንዲያገሉ፣ ራሳቸውን ከምርጫው አናገልም ያሉትን በማሰርና ከስራ በማባረር እንዲሁም ንብረታቸውን በመዝረፍ ላይ እንደሚገኙ የገለጹት አቶ ቶሎሳ በፓርቲው አባላት ላይ የሚደርሰውን ወከባ ለምርጫ ቦርድና ለጋራ ምክር ቤቱ ቢያቀርቡም ሁለቱ አካላት መፍታት እንዳልቻሉ ገልጸዋል፡፡

‹‹በኦህዴድ ካድሬዎች ወከባ የደረሰበት አባላትን ለምርጫ ቦርድ ሪፖርት በማድረጉ፣ ለምን በምርጫ ቦርድ ሪፖርት አደረክ በሚል የኦህዴድ ካድሬዎች ሌሊት ሰብረው ገብተው የሞባይል ሱቁን ዘርፈውታል፡፡›› ያሉት ሊቀመንበሩ ጫናው ከአቅማችን በላይ ሆኗል ብለዋል፡፡

አቶ ቶሎሳ አክለውም ‹‹ወደ ጋራ ምክር ቤቱ ስንገባ አባላቶቻችን ላይ የሚደርሰው ወከባና አፈና ይቀንሳል የሚል እምነት ነበረን፡፡ ሆኖም የጋራ ምክር ቤቱ ህጎቹን ለማስከበር አቅም የለውም፡፡ የጋራ ምክር ቤቱ የተለያዩ ምክንያት እየተጠቀሰ ወርሃዊ ስብሰባውን ማድረግ አልቻለም፡፡ ለይስሙላህ ካልሆነ በስተቀር ጠንክሮ ውጤት ያስመዘግባል የሚል ግምት የለኝም፡፡ ምንም እንኳ እንዲጠናከር ግፊት ብናደርግም እንደተባለው እየተጠቀምንበት አይደለም›› ብለዋል፡፡

The post ኦብኮ በገዥው ፓርቲ ወከባ እየደረሰብኝ ነው አለ appeared first on Zehabesha Amharic.

ምርጫ ቦርድ ሰማያዊ ፓርቲን ከምርጫ ለማገድ ፍላጎት እንዳለው ታወቀ

$
0
0

• ‹‹ሰማያዊ ሳይጠብቁት በመላ አገሪቱ ዕጩ በማቅረቡ ደንግጠዋል›› ኢ/ር ይልቃል ጌትነት

ምርጫ ቦርድ በየወረዳው ለሚገኙ የምርጫ ቦርድ አስፈፃሚዎች ‹‹ከቦርድ የሚጠበቅ ውሳኔ ስላለ፣ ሰኞ ተሰብስበን እስክንወስን ድረስ የሰማያዊ ፓርቲ ዕጩዎቹን ወደ ቅጽ 4 እንዳታዘዋውሩ›› የሚል መልዕክት ማስተላለፉን እና ሰማያዊ ፓርቲ ያቀረባቸውን ዕጩዎች ከመቀነስ ጀምሮ ፓርቲውን ከምርጫው ለማገድ ፍላጎት እንዳለው ከምርጫ አስፈጻሚዎች መረጃዎች ደርሰውናል ሲሉ የፓርቲው ሊቀመንበር ኢ/ር ይልቃል ጌትነት ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡
Hiber Radio Interview with Eng Yilkal Getnet
ፓርቲው ከትግራይ፣ እስከ ሞያሌ ጫፍ ዕጩ ማቅረቡ ለገዥው ፓርቲ ያልተጠበቀና አስደንጋጭ ሆኖበታል ያሉት ኢ/ር ይልቃል በህጋዊ መንገድ እየተንቀሳቀሰ የሚገኘው ሰማያዊ ፓርቲ ላይ የሚደረጉት ጫናዎች ተጠናክረው መቀጠላቸውን ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡ ‹‹ሰማያዊ ሰይጠብቁት በመላ አገሪቱ ዕጩ በማቅረቡ ደንግጠዋል፡፡ በአዲስ አበባ 23 ዕጩዎችን አቅርበናል፡፡ አዲስ አበባ ውስጥ አንድ ዕጩ ያቀረቡ ፓርቲዎች ሳይቀር በሚዲያ ሲነገርላቸው ሰማያዊ ፓርቲ ያቀረባቸውን ዕጩዎች ለመግለጽ ፈቃደኛ አልሆኑም፡፡ ዛሬ ጠዋት ደግሞ የምርጫ ቦርድ ባለስልጣናት በቴሊቪዥን ቀርበው ‹ሰማያዊ በተደጋጋሚ ብንነግረው አልሰማም፣ በመሆኑም ሰኞ ቦርዱ ተሰብስቦ ውሳኔ ያስተላልፋል› ብለዋል፡፡ ይህም የሚያሳየው ሰማያዊ በምርጫው እንዳይሳተፍ ችግር መፍጠር እንደሚፈልጉ ነው፡፡›› ሲሉ ፓርቲው ላይ እየተፈጠረበት ያለውን ጫና ገልጸዋል፡፡

የምርጫ ቦርድ ጽ/ቤት ምክትል ኃላፊ አቶ ወንድሙ ጎላ በዛሬው ዕለት በኢቢሲ ቀርበው ሰማያዊ ይቅርታ ባለመጠየቁና ማስጠንቀቂያዎችን ባለመቀበሉ ነገ ሰኞ ጥር 9/2007 ዓ.ም ውሳኔ ያስተላልፋል ብለዋል፡፡
ከሌሎች ፓርቲዎች ሰማያዊን በመቀላቀል በፓርቲው ምልክት ለመወዳደር የወሰኑ ዕጩ ተወዳዳሪዎች እንዲሰረዙ መደረጉና በሌሎች ዕጩዎች ላይም ከፍተኛ ወከባ እየደረሰባቸው እንደሚገኝ ነገረ ኢትዮጵያ መዘገቧ ይታወሳል፡፡

The post ምርጫ ቦርድ ሰማያዊ ፓርቲን ከምርጫ ለማገድ ፍላጎት እንዳለው ታወቀ appeared first on Zehabesha Amharic.

ማኅበረ ቅዱሳን በሚኒሶታ የቴሌቭዥን ስርጭት ጀመረ

$
0
0

mahibere-kidusan-logo(ዘ-ሐበሻ) በሚኒሶታ የማኅበረ ቅዱሳን የሚዲያ ክፍል ሃላፊ( ተጠሪ) የሆኑት አቶ መለሰ አበበ ለዘ-ሐበሻ እንዳስታወቁት ማኅበረ ቅዱሳን በሚኒያፖሊስ እና በሴንት ፖል ለሚኖሩ ኢትዮጵያውያን እና ትውልደ ኢትዮጵያውያን የሚሆን የቴሌቭዥን ስርጭት ጀመረ::

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስትያን ማኅበረ ቅዱሳን የሚኒያፖሊስ ንዑስ ማዕከል በየሳምንቱ እሑድ በሚኒያፖሊስ እና በሴንት ፖል ከተሞች የቴሌቪዥን ፕሮግራሙን የሚያቀርብባቸው ቻናሎች:-

ሴንት ፖል SPNN Channel 14

እሑድ 12:30pm-1:30pm እንዲሁም እሑድ 7:30pm-8:30pm ሲሆን

በሚኒያፖሊስ MTN ደግሞ

Channel 75 እሑድ ከ9pm-10pm መሆናቸው ታውቋል::

እንደ አቶ መለሰ ገለፃ ከሚኒያፖሊስ እና ሴንት ፖል ከተማ ውጭ ወይም አገር የምትገኙ መርሐግብሩን በተመሳሳይ ስዓት በኢንተርኔት ድረ ገጽ በቀጥታ መከታተል ይቻላል ብለዋል:: የኢንተርኔት አድራሻው Channel 75: http://www.mtn.org/channel 75 ነው::

The post ማኅበረ ቅዱሳን በሚኒሶታ የቴሌቭዥን ስርጭት ጀመረ appeared first on Zehabesha Amharic.

በሚኒሶታ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ለማህሙድ አህመድ ያላቸውን ክብር ገለጹ

$
0
0

(ዘ-ሐበሻ) “የትዝታው ንጉስ” በሚል በኢትዮጵያ ሙዚቃ ታሪክ ላይ በትልቁ ስሙ የሚጠራው ድምፃዊ ማህሙድ አህመድ በሚኒሶታ ደማቅ የሙዚቃ ኮንሰርት አቀረበ::
Mahmud Ahemed – A day filled with tears
74ኛ ዓመቱን የያዘው አርቲስት ማህሙድ አህመድ ትናንት የቫለንታይን ደይን በማስመልከት በሚኒሶታ በተደረገው የሙዚቃ ኮንሰርት ላይ ያሳየው ብቃት ሙዚቃ ምን ያህል አብራው እንደተፈጠረች የሚያሳይ ነው ሲሉ በስፍራው የነበሩ ኢትዮጵያውያን አድናቆታቸውን ገልጸዋል::

ዛሬ በኮምፒውተር ድምጻቸውን እየሞረዱ የሚወጡት አርቲስቶች መድረክ ላይ ሲወጡ በሚሸማቀቁበት ዘመን ማህሙድ የሚታወቅበትን ከትዝታ እስከ ጉራጊኛ ዘፈኖች በማይቀየር ድምጹ ተጫውቶታል ያለን አንድ የሙዚቃ አዋቂ ይህ ዘመን የማይሽረውን ድምፃዊ በዓይኔ ዳግም ከረዥም ዓመታት በኋላ መድረክ ላይ በማየቴ ደስተኛ ነኝ ብሏል::

ማህሙድ ወደ መድረኩ ሲወጣ ሕዝቡ በከፍተኛ ጩኸትና ፉጨት የተቀበለው ሲሆን እርሱም ደረቱን በሁለት እጆቹ በመያዝ ለሕዝቡ ያለውን ፍቅር ገልጿል::

በሚኒሶታ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን በተለይ ለአንጋፋ አርቲስቶች የሚሰጡት ክብር በአረአያነት የሚጠቀስ ሲሆን ከዚህ ቀደምም በተመሳሳይ ቴዎድሮስ ታደሰ ሲመጣ ክብራቸውን ገልጸዋል::

በሙዚቃ ሕይወት ከግማሽ ምዕተ ዓመት በላይ የቆየው ማህሙድ አህመድ ባለፈው ሳምንት በኤድመንተን ካናዳም ተመሳሳይ የሆነ ክብር በሕዝብ ዘንድ ማግኘቱን የዘ-ሐበሻ ዘጋቢዎች ከስፍራው ጠቁመውን ነበር::

በትናንትናው ዕለት በሚኒሶታ በተደረገውና ናዲ ፕሮሞሽን እና ዲጂ ሶሎ ባቀረቡት በዚህ የሙዚቃ ኮንሰርት ላይ በርካታ ሕዝብ ከመገኘቱም በላይ በመሃሙድ ሥራዎች በ እጅጉ ሲዝናና አምሽቷል::

በዚህ ኮንሰርት ላይ ወጣቱ ድምጻዊ ጃኪ ጎሲም ሥራዎቹን አቅርቧል::

ይህን ታላቅ ኮንሰርት ዘ-ሐበሻ በቭዲዮ አስቀርታዋለች – ሕዝቡ ለማህሙድ ያሳየውን ፍቅርም ይመልከቱበት:: ተከታታይ ቭዲዎችን ለማቅረብም እንሞክራለን::

ዘ-ሐበሻ በአንድ ወቅት ያቀረበችውን የማህሙድ አህመድን ታሪክ ለማንበብ እዚህ ይጫኑ

The post በሚኒሶታ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ለማህሙድ አህመድ ያላቸውን ክብር ገለጹ appeared first on Zehabesha Amharic.


‹‹ሰላማዊ ትግሉ ሲጠናከር ስርዓቱ ወደ አውሬነት ይቀየራል››

$
0
0

ነገረ ኢትዮጵያ

ኢ/ር ይልቃል ጌትነት
• ‹‹ቃል ኪዳናችንን ማጥበቅ አለብን!››

(በዛሬው ዕለት ለቀድሞው የአንድነት አመራሮችና አባላት የተዘጋጀው የእንኳን ደህና መጣችሁ አቀባበል ላይ ከተናገሩት)

10994318_665307356928259_3852354460061459043_n

ኢ/ር ይልቃል ጌትነት

ፓርቲ ጣኦት አይደለም፡፡ ኢህአዴግ ቅንጅትንም አፍርሶታል፡፡ አንድነትንም አልፈረሰም ብለው እንዳይከሱኝ እንጅ አፍርሰውታል ማለት እችላለሁ፡፡ በዚህ ሁኔታ ሰማያዊ ላይም አንድ ነገር ማምጣታቸው የማይቀር ነው፡፡ ያ ማለት ግን ሰላማዊ ትግሉ ምን ያህል እንዳስፈራቸው ነው የሚያሳየው፡፡ አገዛዙ በፓርቲዎች ላይ የሚወስደው እርምጃ የሚያሳየው ሰላማዊ ትግሉ መጠናከሩን እንጅ ወደኋላ መመለሱን አይደለም፡፡ አንዳንዶቹ እንዲህ አይነት ችግር ሲከሰት ሰላማዊ ትግሉ አበቃለት ይላሉ፡፡ ሆኖም አገዛዙ ሰላማዊ ትግል አስፈርቶት አውሬ ሲሆን የሚያረጋግጥልን ሰላማዊ ትግሉ መጠናከሩን ነው፡፡

በመሳሪያ ትግል ውስጥ አንድ ጀኔራል ሲሞት አሊያም አንድ የጦሩ አካል ችግር ሲደርስበት ‹‹የትጥቅ ትግል አበቃለት›› እንደማይባለው ሁሉ ሰላማዊ ትግል ላይ አንድ ጫና ወይንም የስርዓቱ ደባ ሲከሰት ትግሉ አይሰራም ማለት አይደለም፡፡

ሰላማዊ ትግል መስዋዕትነት አያስከፍልም ማለት አይደለም፡፡ እንዲያውም ሰላማዊ ትግል ውጤት ማምጣት ሲጀምር፣ ዙሩም ሲካረር፣ የሚከፈለው ዋጋም ይበልጥ እየጨመረ ይሄዳል፡፡ የስርዓቱ አውሬነት በተገለጠ ቁጥር፣ እኛም በተሻለ አመራር ትግሉን ስንመራው መስዋዕትነቱ ይበልጡን እየበዛ እንደሚመጣ እንረዳለን፡፡

በአሁኑ ወቅት ስርዓቱ ሰላማዊ ትግሉ በመጠናከሩ ፍርሃት ውስጥ ይገኛል፡፡ ሰላማዊ ትግሉ ሲጠናከር ስርዓቱ ወደ አውሬነት ይቀየራል፡፡ እስካሁን በሰላማዊ ትግሉ፣ አሁንም በአንድነት ላይ የደረሰው ፈተና የሚያሳየው ሰላማዊ ትግሉ አሸናፊ እንደሆነ ነው፡፡

ዛሬ ያደረግነው ግንኙነት፣ አንድም ለመተዋወቅ፣ በሌላ መልዕክት ለማስተላለፍ፣ ከዚህም በተጨማሪ አንድነታችንን ለማጠናከርና ለትግሉም በቆራጥነት የተዘጋጀን መሆኑን ለማሳየት ነው፡፡ አሁን እዚህ ቦታ የተገናኘን ሰዎች ሰላማዊ ትግሉ ይበልጡን እየተጠናከረ ሲሄድ ምን አልባትም አንድ እስር ቤት የምንታጎር በመሆናችን ቃል ኪዳናችንን ማጥበቅ አለብን፡፡ አንድታችንም የቆየ የፓርቲ ድንበር ሳይገድበን ማጠናከር አለብን፡፡ ከአሁን በኋላ ለሚደርሱብን ችግሮችና እንቅፋቶች ፈጣን መልዕክት እየሰጠን እንቀጥላለን፡፡ ለዚህም የሰማያዊ ፓርቲ አመራር ትግሉን በተገቢው መንገድ እንደሚመራው ማረጋገጥ እፈልጋለሁ፡፡

ሰማያዊ ፓርቲ ውስጥ አንድ የተለመደ ባህል አለ፡፡ በሰማያዊ ቤት ሁሉም ሰው ጓደኛ ነው፡፡ ሁሉም ሰው እኩል ነው፡፡ ማን የማን ጓደኛ መሆኑ አይታወቅም፡፡ የምክር ቤት አባል፣ ኦዲት፣ ስራ አስፈጻሚ፣ ተራ አባል የሚባል ነገር የለም፡፡ በሰማያዊ ቤት ስልጣን ለግንኙነት ምንም አይነት ችግር አይፈጥርም፡፡ አብዛኛዎቹን የአንድነት አባላት አውቃቸዋለሁ፡፡ ይህ የሰማያዊ ፓርቲ ባህል ጋርም ተላምዳችሁ፣ ጥያቄና ሀሳብ ሲኖራችሁም በግልጽ ማቅረብ የምትችሉበት ቤት ነው፡፡ በዚህ መልክም ጠንክረንና ቃል ኪዳናችን አድሰን ትግላችን ማስቀጠል አለብን፡፡ ለምንጓዝበት የተራራ ጉዞም ወገባችን ጠበቅ፣ ልባችን ሞቅ አድርገን በቃል ኪዳናችን ፀንተን ለምንወዳት አገራችን ትግላችን አጠናክረን እንድንቀጥል ጥሪዬን አስተላልፋለሁ፡፡

‹‹አንድነትን ያሳጣኝ ኃይል ለእኔ ጠላቴ ነው››

ወጣት ስንታየሁ ቸኮል (የቀድሞው አንድነት ወጣቶች ጉዳይ)

አንድነት የኢትዮጵያን ፖለቲካ መቀየር የሚችሉ ምሁራንና ታጋዮች የያዘ ፓርቲ ነበር፡፡ አንድነት የኢትዮጵያን ያለባትን ችግር የሚገባ የሚረዱ ወጣትና ሴቶችም ስብሰብ ያለው ፓርቲ ነበር፡፡ አንድነት በነበረው ቁመና ምን አልባትም የመንግስትን ስልጣን መቀበል የሚያስችል አቅም የነበረው ፓረቲ ነው፡፡ አንድነትን ማፍረስ የተፈለገው አንድነት በነበረው አቅም ቢቀጥል ህወሓት/ኢህአዴግ ስልጣኑን እንደሚለቅ ስለሚያውቀው ነው፡፡ አንድነት ያፈረሱት ፓርቲው ውስጥ ምንም አይነት ችግር ኖሮ ሳይሆን ስርዓቱ ስለፈራው ነው፡፡ አንድነት ፕሬዝደንቱን የሰየመው በጠቅላላ ጉባኤው ነው፡፡ አሁን ግን ፕሬዝደንቱ ከኢህአዴግ ጽ/ቤት ነው የተመደበው፡፡ ይህን ከኢህአዴግ ጽ/ቤት የተመደበውን ፕሬዝደንት ነው በቀጥታ ተቀበሉት የተባልነው፡፡ እኛ ደግሞ አንቀበልም፡፡ ያልተቀበልነውና ወደሰማያዊ የመጣነው ሰላማዊ ትግሉ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ለማሳየት ነው፡፡

የአንድነት አባላት ወደ ሰማያዊ ፓርቲ ሲመጡ ለፕሮግራምና ለመሳሰሉት ጥቃቅን ነገሮች እየተጨነቁ አይደሉም፡፡ እኛ ወደዚህ የመጣነው በቁጭት ነው፡፡ አንድነትን ያሳጣኝ ኃይል ለእኔ ጠላቴ ነው፡፡ ይህን ጠላት ለመታገል ነው የመጣሁት፡፡ ጥቃቅን የፕሮግራም ልዩነቶች ይህን ትግሌን አያደናቅፈውም፡፡ ስርዓቱ ሰላማዊ ትግል አይቻልም፣ ሲለን እኛ ደግሞ እንዴት እንደሚቻል እናሳየዋለን፡፡ ወደሰማያዊ የመጣንበት ዋነኛው አላማ ይህ ነው፡፡ እኔ በበኩሌ ከሰማያዊ ፓርቲ ወጣቶች ጋር መተዋወቅ አይጠበቅብኝም፡፡ አውቃቸዋለሁ፡፡ እንዲያውም ወደ ቤታችን እንደመጣን ነው የሚሰማኝ፡፡ የጊዜ ጉዳይ መልሶ አገናኝቶናል፡፡ የዚህ አገር ችግር ምን እንደሆነ እናውቀዋለን፡፡ ከዚህ በኋላ የምናደርገው ትግል የነጻነት ትግል ነው፡፡ ወደ ሰማያዊ በመጣንበት ወቅት ከሊቀመንበሩ ጀምሮ በጣም ደስ በሚል ሁኔታ ተቀብለውናል፡፡ ዛሬም በተመሳሳይ መልኩ በጣም ደስ የሚል አቀባበል አድርገውልናል፡፡ ወደፊትም ለምናደርገው ትግል በተመሳሳይ መንፈስ እንደምንቀጥል ተስፋ አለኝ፡፡

The post ‹‹ሰላማዊ ትግሉ ሲጠናከር ስርዓቱ ወደ አውሬነት ይቀየራል›› appeared first on Zehabesha Amharic.

እየከፋ በመጣው የሰብአዊ መብት ረገጣ ላይ የጋራ አቋም መግለጫ ከፖለቲካ ፣ ሲቪክ ፣ የሃይማኖት ድርጅቶችና ታዋቂ ግለሰቦች

$
0
0

«ለውጥ በማይቆም ተሽከርካሪ የሚጓዝ አይደለም፤ የተከታታይ ትግል ውጤት ነው። ነጻነት የምንፈልግ ሁሉ ጀርባችንን ቀና አድርገን መታገል አለብን። ራሳችን ካልፈቀድንለትና ካልተሸማቀቅን፤ ማንም ሰው እንደ ከብት ሊጋልበን ከቶ አይችልም” ነበር ያሉት ዶር ማርቲን ሉዘር ኪንግ ጁኔር ።

በማንኛውም አገር ቢሆን፣  ነጻ የሆነ የዜና አገልግሎት የማያገኝ፤ ተቆርቋሪ የፖለቲካ ወይንም የማህበረሰብ ወይንም የሲቪክ ድርጅት እና በነጻነት የሚንቀሳቀስ የመገናኛ ብዙሃን አገልግሎች የሌለው  ሕዝብ መብት የለውም። መብቱ በመንግሥት የተከለከለ ግለሰብ ሆነ ቡድን፤ ማህበረሰብ ሆነ ሕብረተሰብ ዘላቂነትና ፍትሃዊነት ያለው እድገት አይጎናፀፍም።

ሕወሃት/ኢሕአዴግ ለሃያ አራት ዓመታት በበላይነት ሲገዛት የቆየችዋ ኢትዮጵያችን  ፍትህ፤ ነጻነት፤ ሰብአዊ መብት፤ የሕግ የበላይነት  የማይታይባትና  አምባገነናዊ ስርዓት የሰፈነባት ሃገር ሆናለች። ምንም እንኳን ኢትዮጵያ የመድበል ፓርቲ ስርዓት የምትከተል መሆኗ በሕግ መንግስቱ ቢደነገግም፣ በተግባር የታየው ግን ከገዝው ሕወሃት/ኢሕአዴግ ነጻ የሆኑ ድርጅቶችን ሁሉ የማጥፋት ሂደት ነው። የአገሪቷን ሕግ ሆነ የምርጫ ቦርድን አሰራር  በጣሰ መልኩ፣ በቅርቡ በአገሪቷ ጠንካራ የሚባለውን የአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት)  አመራርን በማገድ ራሱ ያቋቋማቸዉን ተለጣፊ መሪወች መሾሙ፣ ሕወሃት/ኢሕአዴግ  በምርጫ የማያምንና፣ ብቻውን ለሚቀጥሉት ሃያ፤ ሰላሳ አመታት በጉልበት ለመግዛት እንደወሰነ አመላካች ነው። የዜጎችን የመደራጅትና የመሰባሰብ ሰባአዊ መብትም የረገጠ ነው።

በአንድነት ፓርቲ ላይ ከታየው የሕወሃት/ኢሕአዴግ ያገጠጠ ኢፍትሃዊ እርምጃ በተጨማሪ፣ በሌሎች የፖለቲካና የሲቪክ ማሀብራት ላይ አፈናዉና የመብት ረገጣው ተባብሷል፡፡በህጋዊነት የሚንቀሳቀሱ ድርጀቶች ሁሉ ህልውናቸው አደጋ ላይ ነው። ዜጎችን ሕገ መንግሥቱ በሚፈቅደው መሰረት ሰላማዊ ሰልፍ ሲያደርጉ ይደበደባሉ። ጋዜጠኞች የሰባዊ መብት ተሟጋቾች፣ የሃይማኖት መሪዎች ይታሰራሉ።

ሕወሃት/ኢሕአዴግ  በሚያራምዳቸው የተሳሳቱ የኢኮኖሚ ፖሊሲዎች ዜጎች  ባስከፊ በድህነት እና የኑሮ ዉድነት ስቃይ ዉስጥ እንዲዘፌቁ አድርጓቸዋል። የስራ እድል ማጣት፤ የተፈጥሮ ሃብት ከኢትዮጵያዊያን ተነጥቆ ለጥቂቶች ሃብት ማካበቻ መሆን፤ የጎሳ አድልዎ፤ ጉቦ፤ ሙስና፤ በብዙ ቢሊዮን የሚቆጠር ገንዘብ ከሕግ ውጭ ማሸሽ፤ በኢትዮጵያዉያን መካከል ስርዓት ወለድ የሆነ የጎሳና የኃይማኖት መለያየት በአገራችን ትልቅ ቀዉስን እና ዉስጣዊ አለመረጋጋትን ፈጥሯል። ከመቼዉም ጊዜ በላይ አገራችን ትልቅ አደጋ ላይ ትገኛለች።

መንግስት የሕዝብ አገልጋይ ሊሆን ይገባዋል። ህወሃት/ኢሕአዴጎች ግን በመንግስት ወንበር ላይ ተቀምጠው ህዝብን ማገለገል ሳይሆን ህዝቡን እየከፋፈሉትእና  እያሰቃዩት ነው። ለሃያ አራት አመታት በህዝብ እና በሀገር ላይ እጅግ ብዙ በደል ፈጽመዋል።  ይህን ለማስቆም ኢትዮጵያዉያን ቆርጠንና  ደፍረን፣  አገር አቀፍ በሆነ ደረጃ መነሳት ይኖርብናል። በውጭና በውስጥ የምንገኘው ለውጥ እና ፍትህ ፈላጊ  ኃይላት፣ አብረን ተባብረን መስራት ግዴታችን ሆኗል። ሕወሃት የሚፈልገው በየተራ ለማጥቃት እንዲያመቸው በተናጥል የሚደረግን  ትግል ነው። ትግሉ የመኖር ያለመኖር፤  የህልውና ጉዳይ ስለሆነ አብሮ ተያይዞ መነሳት የወቅቱ መሪ ጥያቄ ነው።

እኛ ስማችን ከዚህ በታች የተዘረዘረው ስብስቦች እንደዚህ ያለ ተከታታይ ግፍ በኢትዮጵያ ሕዝብ ላይ ሲካሄድ በአንድ ላይ ድምፃችን ማሰማት ግዴታችን ነው እንላለን። ስለሆነም፤

  1. በቅርቡ የአንድነት ፓርቲ አመራር አባላትን ህገወጥ በሆነ መንገድ የገዝው ቡድን መሳሪያ በሆነው የምርጫ ቦርድ አማካንነት ከሀላፊነታቸው በግዳጅ አባሮ በአባላት ያልተመረጠ ግለስብ በመሪነት መሾሙን አጥብቀን እናወግዛለን። ለዚህ በስርአቱ ለተሾመ ግለሰብም፣ እውቅና የማንሰጥ ሲሆን ሁሉም ኢትዮጵያዊ ትብብር እንዲነፍገው እንጠይቃለን። የተለጣፊው ቡድንም፣ ሊወድቅ የተቃረበን የግፍ አገዛዝ ለማገለገል በወሰዳቸው አሳፋሪ ተግባራትም ተጠያቂ እንደሚሆን ለማሳሰብ እንወዳለን።
  2. ስርአቱ በመኢአድ የውስጥ ጉዳይ ጣልቃ በመግባትና በቀጣይ የከፋፋይነት ስራ ድርጅቱን ለማዳከም የሚያካሂደውን ሁሉ ተገንዝበናል። ይህ የገዥው እኩይ ተግባር እውን የሚሆነው በከፊል በድርጅቱ ውስጥ ያሉትን ችግሮች በመመካከር ማስወገድ ሳይቻል ሲቀርና ለገዥው ቡድንም ጣልቃ መግባት መንግድ ሲከፍት እንደሆነ በመገንዘብ፣ ሁሉም የድርጅቱ መሪወችና አባላት ውስጠ ድርጅት ቅራኔወችን በውስጥ አሰራር፣ በመቻቻል፣ በሆደሰፊነትና በተለመደ ሀገራዊ ጨዋነት በመፍታት ሁሉም የድርጅቱ አባላት እንዲሰባሰቡና ታሪካዊ ሀላፊነታቸውን በጋራ እንዲወጡ  እናበረታታለን።
  3. ገዥው ቡድን በአንድነት ፓርቲ ላይ የማፈራረስ እርምጃ ሲወስድ የድርጅቱ አባላት ፣ ተስፋ ቆርጠው፣ ትግሉን እርግፍ አድርገው እንዲያቆሙ ወይም ሀገር ጥለው እንዲሰደዱ ለማድረግ ነው። ይህን በማድረግም አላንዳች ተቀናቃኝ ሁሉንም ተቆጣጥሮ በህዝባችን እና በሀገራችን ላይ የጀመረውን የግፍ አገዛዝ ለመቀጠል ነው። ሆኖም ሁላችንም እንደተመለከትነው አፍራሹን ህወሀት/ኢህአዴግን በሚያሳፍር ለውጥ ፈላጊውን ደግሞ በሚያኮራ መልክ በአዲስ አበባም ሆነ በክልል ያሉ በዛ አሉ የአንድነት አባላት አሁንም ትግሉን ለመቀጠል ወደ ሰማያዊ ፓርቲ እየተቀላቀሉ መሆናቸውን እንገነዘባለን። በዚህ እጅግ ፈታኝ በሆነ ሰዓት ከድርጅት በላይ ሀገርንና ነጻነትን በማሰቀደም በወሰዱት ቆራጥ እርምጃ ያለንን አድናቆት እየገለጥን ወደ ሰማያዊ ያልተቀላቀሉ ጥቂት የአንድነት አባላትም የአንድነትና የዴሞክራሲ ሀይሎችን በመቀላቀል ትግላቻውን እንዲቀጥሉ እናበረታታለን።
  4. ሁሉም የአንድነትና የዴሞክራሲ ሀይሎች የህወሀት/ኢህአዴግን ቀጣይ አፈና መቋቋም የሚቻለው ተነታጥሎ ሳይሆን በጋራ በመቆም እንደሆነ በመገንዘብ አሁንም ትብብራቸውን አጠናክርው ትግላቸውን እንዲቀጥሉ እናሳስባለን። በአፋኙ የህወሀት/ኢህአዴግ ስርአት ስር ለሀገር አንድነት፣ለህዝብ መብት መከበርና ግፈኛውና ከፋፋይ ስርአት ተደምስሶ በምትኩ ለህዝብ ሙሉ መብት መከበር፣ ለሀገር እንድነትና፣ ዴሞክራሲያዊ ህገ መንግስታዊ ስርአትን ለመመስረት ለሚደረገው ትግል ያለንን አጋርነት በጋራ እናረጋግጣለን።

ነጻነት ዋጋ ያስከፍላል። ነጻነት ስለተመኘናት አትመጣም። የኛ እጅ ለእጅ መያያዝና መተባበር የአምባገነኖች ፍጻሜ መጀመርያ ነው። በመሆኑም በተጨበጡ ሥራዎች ዙሪያ ትብብራችንን እያጠናከረን፣ አገር ቤት ለሚደረገው ትግል ሙሉ ድጋፍ እያሳየን፣ የኢትዮጵያ ህዝብ አካል እንደመሆናችን የህዝባችን ነጻነት እስኪያረጋግጥ ከመቼውም ጊዜ በላይ ሳንታክት በጽናት የምንታገል ስለመሆናችን ቃል ኪዳናችንን እናድሳለን።

  1. የሴቶች  የሰብዓዊ መብት ድርጅት
  2. የኢትዮጵያ ሽግግር ምክር ቤት
  3. የሰማያዊ ድጋፍ ማሀበራት
  4. የአንድነት የስዊዱን ድጋፍ ማህበር
  5. የአንድነት የለንደን ድጋፍ ማሀብር
  6. የኢትዮጵያ ድንበር ጉዳይ ኮሚቴ
  7. ሞዓ አንበሳ
  8. የኢትዮጵያ ፖለቲካ እስረኞች አንድነት ድርጅት በካናዳ (ሶሴፕ ካናዳ)
  9. ጋሻ ለኢትዮጰያ የሲቪክ ድርጅት
  10. ኢትዮጰያዊነት የሲቪክ ድርጅት
  11. ኢትዮ ሶሊዳሪቲ ሚኔሶታ
  12. የአንድነት የሰሜን አሜሪክ የሚልዮኖች ድምጽ ለነጻና ፍትሀዊ ምርጫ ኮሚቴ
  13. የኢትዮጵያ ህዝብ የጋራ ትግል ሽንገፐ (በስሩ የሚገኙት አባል ድርጅቶች ሁሉ)
  • የኢትዮጵያሕዝባዊ አብዮታዊ ፓርቲ (ዴሞክራሲያዊ)
  • የኢትዮጵያመድህን ዲሞክራሲያዊ ፓርቲ (መድህን)
  • ትግራይዴሞክራሲያዊ ትብብር (ትዴት)
  • መላኢትዮጵያ ሶሻሊስት ንቅናቄ (መ.ኢ.ሶ.ን)
  • የኢትዮጵያሲቪክ ማህበራት ስብስብ በእንግሊዝ ሀገር
  • የኢትዮጵያየፖለቲካ እስረኞች አንድነት ኮሚቴ (ኢፓእአኮ)
  • ኢትዮጵያሲቪል ኅብረተሰብ ደጋፊዎች በለንደን ኦንታሪዮ

 

Ethiopia

The post እየከፋ በመጣው የሰብአዊ መብት ረገጣ ላይ የጋራ አቋም መግለጫ ከፖለቲካ ፣ ሲቪክ ፣ የሃይማኖት ድርጅቶችና ታዋቂ ግለሰቦች appeared first on Zehabesha Amharic.

የኢሳያስ ቃለመጠየቅና የብሔርተኞች ጫጫታ

$
0
0

ቶኮላ

isayas afewerkiኢሳት ወደ ኤርትራ ተጉዞ የኤርትራውን ፕሬዝዳንት ማናገሩ ከተሰማ ወዲህና በተለይም የቃለመጠይቁ ቅንጣቢ ከቀረበ ቦኋላ እየበገኑ ያሉት ወያኔዎች ብቻ ሳይሆኑ በወያኔ የብሄር ፖለቲካ እናተርፋለን ብለው ሲዳክሩ አመታት ያስቆጠሩ ብሄርተኞች ጭምር መሆናቸውን ጭፍሮቻቸው በሶሻል ሚዲያ ላይ ለማስተጋባት ከሚሞክሩ አስተያየቶች ለማየት እየቻልን ነው:: “በሚንልኪ ዘመን የደነቆረ በሚንልክ እየማለ ይኖራል” እንደተባለው እነዚ ሰዎች ከመንደርተኝነት ተላቀው አለማችን ከቀዝቃዛው ጦርነት ፍጻሜ ወዲህ የደረሰቺበትን እድገት ምነው መረዳት ተሳናቸው? የሚል ጥያቄ ያስጨንቀኝ ጀምሮአል:: በኤኮኖሚ የበለጸጉት የአውሮጳ አገሮች ብንዋሃድ ነው በአለም ውስጥ ተገቢ ስፍራችንን ይዘን መቀጠል የምንችለው በማለት አንድ ለመሆን ሲጣደፉ የኛዎቹ በቋንቋ ተካለን የየራሳችንን የፖለቲካ ጎጆ ብንቀልስ ነው የሚበጀን ማለታቸው የጤና ነው?

ከሁሉም የሚገርመው ሰው በሰውነቱ በተከበረበት አለም እየኖሩ ለአገራቸውና ለህዝባቸው ግን የሚመኙት ሰው በቋንቋ ማንነቱ እርስ በርሱ የሚጠፋፋበትን የጥንትዮሽ ዘመን አይነት አስተዳደር መሆኑ የሰው ደም የሚያስጠማቸው ምን አይነት መንፈስ ብጠናወታቸው ነው? ያስብላል:: ቋንቋና ባህል ሰው በተወለደበት ህብረተሰብ ውስጥ የሚማረውና ይዞት የሚያድገው ትርጉምና ጥቅም የሚሰጠውም በዚያው ህብረተሰብ ውስጥ እስከተኖረ ድረስ ብቻ ሆኖ ሳለ ሌላው ቀርቶ አሜሪካና አውሮፓ ውስጥ ከአብራካቸው የሚወለዱት ወይም የተወለዱት ሳይቀሩ እነርሱ የኛ ነው የሚሉትን የማይወርሱ መሆናቸውን እያወቁ ለምንድነው አመለካከታቸውን መቀየር የተሳናቸው?

እኔን የሚያሳዝነኝ የመልካም አስተዳደር እጦት ለምድራዊ ጉስቁልና የዳረገው መከረኛ ህዝብ በቋንቋና በባህል ልዩነት ምክንያት እርስ በርሱ ቢገዳደል ምንድነው ጥቅሙ? የምሥራቅ አውሮፓዎን የቅርብ ጊዜ ትዝታ ትተን አይናችን ፊት በሩዋንዳ፤ በቡሩንድ፤ በሱማሌ ወዘተ ህዝብ እርስ በርስ መጠፋፋት ማን ተጠቀመ? እንዴት ከዚህ መማር ይሳነናል?

አያት ቅድሜ አያቶቻችን በመሰዋዕትነት ባስረከቡን ነጻ አገር ውስጥ ተወልደንና አድገን የአስተዳደር በደል ያስከተለውን ኢፍትሃዊነት ከመዋጋትና የጋራ ቤታችንን ከድህነትና ከመብት ረገጣ የጸዳ ከማድረግ ይልቅ እራሳችንን የሚያሳንስ ለሌላው ግን የሌለ ኩራትና ክብር የሚፈጥር ” የጥቁር ቅኝ ገዥ” ታሪክ በራሳችን ላይ መፍጠር ለምን አስፈለገ?

መለስ ዜናዊና የበታቸኝነ ስሜት የፈጠራቸው ጥቂት የትግራይ ጉጂሌዎች ከፋፍሎ ለመግዛት በሸረቡት ሤራ ተተብትበን እስከመቼ እንታለላለን? በኔ አስተያየት በብሄርተኝነት ዙሪያ ጫፍ የረገጥ ፖለቲካ የሚያቀነቅኑ ሰዎች በተለያየ ምክንያት በግለሰብ ደረጃ የበታቸኝነት ስሜት ውስጥ የተዘፈቁ ናቸው:: ምናልባት ዘመናዊ ትምህርት ችግሩን ሳያባብሰው አልቀረም:: የሥነልቦና ሙያተኛም ባልሆን የበታቸኝነት ስሜት የሚጠፋው ከውስጥ ተኮትኩቶ በሚወጣ የራስ መተማመን ብቻ ነው ብየ አምናለሁ:: እራስን ማከም ለሚቻል የስነልቦና ችግር አንድ ሚስኪን ከሌላው ሚስኪን የአገሩ ዜጋ ጋር እንዲገዳደል ማነሳሳት ወንጀል ነው::

ስለዚህ ለአገርና ለወገን የማይበጅ የኦሮሞ፡ የትግሬ፡ የሱማሌ ፡የሲዳማ፡የአማራ ወዘተ ብሄርተኝነት ከማቀንቀን እኔ በቋንቋዬ ፡ በሃይማኖቴ ፡በባህሌ ወይም በመልኬ ምክንያት ከማንም በታች አይደለሁም:: ያነስኩ ሆኘ እራሴን አይቼ ቢሆን እንኳ ያለፉት ኋላ ቀር አገዛዞች ጭነውብኝ ያለፉት ስለሆነ የዚያ ሠለባ ለመሆን እራሴን አሳልፌ አልሰጥም የሚል በራስ መተማመን ከውስጥ ሊመነጭ ይገባል:: በሠለጠነው 21ኛው ክፍለ ዘመን እኔን ከራሱ አሳንሶ የሚያየኝ ካለ በድንጋይ ዘመን ከነበሩት እነዚያ አገዛዞች የባሰ ኋላቀር ነው ብሎ የሰው መሳቂያ መሳለቂያም ማድረግ ይቻላል:: ኢሳያስ አፈወርቂ አሉም አላሉም የብሄር ፖለቲካው ምን ያህል እንደጎዳንና እንዳዳከመን ስላወቅን ነው የብሄር ፖለቲካው ላይ የትግል ክንዳችንን ለማንሳት የተገደድነው:: የብሄር ብሄረሰቦች ቀን እንድናከብር አድርጎን በሌላ በኩል ግን በታሪክ ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ ለብሄር ጭቆና የዳረገንና የኢትዮጵያ እስር ቤቶች ኦሮሚኛ ተናጋሪ ሆኖአል እስከመባል ያደረሰንን ሥርዓት የምንዋጋው ያለምክንያት አለመሆኑን ወያኔ ራሱ ተረድቶታል:: በብሄራችን ምክንያት ብቻ ከሥራ መፈናቀል፡ለእሥር፡ ለስደትና ለሞት የተዳረገን ሁሉ ሳንለያይና ሳንከፋፈል ዘረኛውን አገዛዝ ከጫንቃችን ለማውረድ ጊዜው አሁን ነው:: አገራችንን የዘረፈ፡ የመጭውን ትውልድ ሳይቀር ዕድል ለማጨለም አገራችንን ለም መሬት እየሸነሸነ ለባዕድ እየቸበቸበ ያለውን ወያኔን በምንም መስፈርት ከኢሳያስ አፈወርቂ ጋር አናወዳድርም :: ምንም እንኳ ኢሳያስ የዛሬዎቹን ጨቋኞቻችንን ለድል ለማብቃት አስተዋጽ ቢኖራቸውም ዋናው ለአገራችንና ለሁለቱ ህዝቦች ቅን እንደሚያስቡ ከአንደበታቸው መስማታችን ለኔ በቂ ነው:: ደግሞ ሰው ይሳሳታል ዋናው ከስህተቱ ለመማርና ስህተቱን ለማረም ዝግጁ መሆኑ ነው:: ፕረዝዳንት ኢሳያስን የወደድኩት ይህንን ስላረጋገጡልኝ ነው ::

እናንተስ ምን ትላላችሁ?

The post የኢሳያስ ቃለመጠየቅና የብሔርተኞች ጫጫታ appeared first on Zehabesha Amharic.

የዲሞክራሲዊ ለውጥ በኢትዮጵያ ድጋፍ ድርጅት ኖርዌይ የአቶ አንዳርጋቸው ፅጌ 60ኛ አመት የልደት በአል በተሳካ ሁኔታ ተከናወነ

$
0
0

በፌብርዋሪ 14, 2015

አጠቃላይ የአባላት ስብሰባ 

unnamed (3)

ፌብርዋሪ 14, 2015 በኖርዌይ የሚኖሩ የዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ ድጋፍ ድርጅት ኖርዌይ መተዳደሪያ ደንቡ በሚያዘው መሰረት የአባላት ጠቅላላ 3ኛ  እና 4ኛ ሩብ ዓመት መደበኛ ስብሰባ የሥራ ክንውን ሪፖርት የቀረበበት የተሳካ አጠቃላይ ስብሰባ አድርገዋል። በስብሰባው ላይ በኖርዌይ ዋና ከተማ ኦስሎና በተለያዩ የኖርዌይ ከተሞች የሚኖሩ የድርጅቱ አባላቶች የተገኙ ሲሆን የአባላት ስብሰባው አስቀድሞ በተያዘለት ፕሮግራም መሰረት በኖርዌጂያን የሠዓት አቆጣጠር ከቀኑ 13፡30 ተጀምሮዋል።

 

ስብሰባውን የዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ ድጋፍ ድርጅት በኖርዌይ ህዝብ ግንኙነት ኃላፊ የሆኑት አቶ አቢ አማረ በ 24 ዓመት የወያኔ አረመኒያዊ አገዛዝ በግፍ ለተገደሉት እና በየእስር ቤቱ በግፍ ለሚስቃዮ ንጹሀን ዜጐች የአንድ ደቂቃ የህሊና ጹሎት በማድረግ ስብሰባውን ያስጀመሩ ሲሆን በመቀጠልም የዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ ድጋፍ ድርጅት በኖርዌይ ሊቀመበር አቶ ዮሐንስ አለሙ አባላቱን እንኳን ደህና መጣችሁ በማለት ንግግር አቅርበው የዛሬው የአባላት ስብሰባ ከሌሎቹ ጊዜያት በሁለት ምክንያቶች የተለየ መሆኑን ለተሰብሳቢው ገልፀዋል ይሄውም፦

  • የአቶ አንዳርጋቸው ፅጌ 60 ኛ ዓመት የልደት በአል የሚከበር መሆኑና

 

  • የዲሞክራሲ ለውጥ በኢትዩጵያ ድጋፍ ድርጅት በኖርዌይ የተመሰረተበትን 10ኛ አመቱ ላይ መገኘቱ እንደሆነ በማስረዳት ድርጅቱ በእነኚህ አስር ዓመታት ውስጥ ብዙ አመርቂ ስራዎችን እንደሰራና ቅንጅት ይዞለት የተነሳው አላማ እስከ አሁን ድረስ ይዞ በመጓዝ ላይ ያለ ድርጅት በመሆኑ ኩራት የሚሰማቸው መሆኑን በመግለፅ ይህንንም አላማ ከግብ ለማድረስ በድርጅቱ ውስጥ ያሉ ወጣቶች እየሰሩ ያለውን በማድነቅ ወጣቶች ወያኔን ከስልጣን ለማስወገድ ትልቅ አስተዋፅኦ ያላቸው በመሆኑ ትግላቸውን አጠንክረው መቀጠል እንዳለባቸው ተናግረዋል። ሊቀመንበሩ በንግግራቸው መጨረሻ አቶ አንድአርጋቸው ፅጌንና ሌሎችም በግፍ የታሰሩ የፖለቲካ እስረኞችን በትግላችን እናስፈታለን ብለዋል።

unnamed (2)በመቀጠል የተለያዩ የስራ ክፍል ኃላፊዎች የስድስት ወር የስራ ክንውን ረፖርት ለአባላቱ ያቀረቡ ሲሆን ከበርገን፣ ከስታቫንገር፣ እና ከትሮንዳይም የመጡ የዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ ድጋፍ ድርጅት  በኖርዌይ የስራ ኃላፊዎች በስድስት ወር ውስጥ ስለሰሩት ስራዎች እና ወደፊትም ሊሰሩ ያቀዱትን ስራዎች ለአባላቱ በዝርዝር አስረድተዋል።

ከአባላቱ የተለያዩ ጥያቄዎች የቀረቡ ሲሆን በድርጀቱ ሊቀንበሩ አማካኝነት ማብራሪያ የተሰጠባቸው ሲሆን፣ በመቀጠል የዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ የድጋፍ ድርጅት በኖርዌይ የሚረዳቸው ድርጅቶችን በማስመልከት በድርጅቱ በተወከሉት ሠዎች አማካኝነት ስለድርጅቶቹ አላማ እና ድርጅቶች እየሰሩ ስላሉት ስራዎች ሰፋ ያለ ግምገማ አቅርበዋል።

ግንቦት ሰባትን በመወከል ዶ/ር ሙሉዓለም አዳም ንግግር ያደረጉ ሲሆን በቅርቡ ግንቦት 7 ከአርበኞች ጋር ውህደት እንደፈጠሩ በመግለፅ ውህደት ያስፈለገበትንና የውህደቱን ጠቀሜታ በመግለፅ ግንቦት 7 የፍትህ የነጻነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ የሚለው ስምም አርበኞች ግንቦት 7 የፍትህ የነፃነት የዲሞክራሲ ንቅናቄ በሚል መተካቱን በመናገር ድርጅቱን እየመሩ ያሉትን አመራሮች እነማን እንደሆኑ ለአባላቱ አስተዋውቀዋል ።

የዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ የድጋፍ ድርጅት በኖርዌይ እየደገፈ ያለውን የሰማያዊ ፓርቲ አላማ እና እየሰራ ያለውን ስራ ሰፋ ያለ ማብራሪያ ያቀረቡት ደግሞ አቶ ተዘራ ሲሆኑ የሰማያዊ ፓርቲ ከአረመኔያዊው የወያኔ መንግስት የተለየ ወከባ እንደሚደርስበትና የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮችም ሆነ አባላቶች በወያኔ እየደረሰባቸው ያለውን ጫና በመቋቋም ትግላቸውን  አጠናክረው በመቀጠል ላይ እንደሆኑ በማስረዳት ወደፊትም ዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ የድጋፍ ድርጅት በኖርዌይ አባላቶች ድጋፋቸውን አጠናክረው መቀጠል እንደሚገባ አስገንዝበዋል።

unnamed (1)ስለ አንድነት ፓርቲ አጠር ያለ ንግግር ያደረጉ አቶ ዮሐንስ  ሲሆኑ እሳቸው በወያኔ መሰሪ ሴራ አንድነት ፓርቲ በመፍረሱ እንዳዘነኑና ነገር ግን ዘጠና ከመቶ የሚሆኑት የአንድነት አባላትም ሆነ አመራሮች ሠማያዊ ፓርቲን መቀላቀላቸውን ጠቅሰው ይሄም እንዳስደሰታቸውና ለጊዜው አንድነትን መደገፋቸውን በማቆም የዲሞክራሲያዊ ለውጥ የድጋፍ ድርጅት ኖርዌይ አላማ ጋር ተመሳሳይነት ያላቸው ድርጅቶች ሠማያዊ ፓርቲ እና አርበኞች ግንቦት 7 ድርጅቶችን በመደገፍ እንደሚቀጥሉ አባላቱ በአንድነት ድምፅ ወስነዋል። ከዚህ በፊት የዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ የድጋፍ ድርጅት ኖርዌይ አንድነት ፓርቲን፣ ሰማያዊ ፓርቲ እና ግንቦት ሰባትን ሲደግፉ መቆየታቸው ይታወቃል።

በመጨረሻ የዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ የድጋፍ ድርጅት በኖርዌይ ምክትል ሊቀመንበር አቶ ዳንኤል አበበ የመዝጊያ ንግግር አድርገው የአባላት ስብሰባው 16፡30 ተጠናቋል።

በመቀጠልም የአቶ አንዳርጋቸው ፅጌን 60ኛ አመት የልደት በአል አከባበር የዲሞክራሲያዊ ለውጥ ድጋፍ ድርጅት ሊቀመንበር አቶ ዮሀንስ የመክፈቻ ንግግር አድርገው ስለአቶ አንዳርጋቸው አጭር ንግግር በማድረግ ዝግጅቱን አስጀምረዋል። የአንዳርጋቸውን ታሪክ የሚዳስስ አጭር ፊልም በወጣቶች ክፍል የቀረበ ሲሆን በመቀጠልም አቶ  አንዳርጋቸው ፅጌ ማን ነው? በሚልህይወትታሪኩ ዙሪያ እና ለሀገሩ ያደረጋቸውን የትግል ተሞክሮዎች በቅርበት ከሚያውቋቸው ሰው ሰፋ ያለ ማብራሪያ ቀርቧል። እንዲሁም አቶ አንዳርጋቸውን የሚያወድሱና ስለጀግንነቱ የሚያወሩ የተለያዩ ግጥሞችም ቀርበዋል።

በመጨረሻም የአቶ አንዳርጋቸው ፅጌን ምስል የያዙ ኬኮች ከድርጅቱ ዋና ፅፈትቤት እና ትሮንድላንድ ቅርንጫፍ ፅፈትቤት አማካኝነት የተዘጋጀ ሲሆን በድርጅቱ ሊቀመንበር እንዲሁም በወጣቶችና ሴቶች ክፍል ተወካዮች የመልካም ልደት ኬኩ ተቆርሶ ስነስርአቱ በአቶ አንዳርጋቸው ፅጌ በተደረሰው ላንቺ ነው ሀገሬ ላንቺ ነው ላንቺ ነው ኢትዮጵያ ላንቺ ነው በሚለው ዝማሬ ዝግጅቱ በተሳካ ሁኔታ በኖርዌጅያን የሰአት አቆጣጠር ከምሽቱ 22፡00 ተጠናቋል።

በመጨረሻ የዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ የድጋፍ ድርጅት በኖርዌይ ወጣቶች ፕሮግራሙን በመዘጋጀትና

በመምራት ላደረጉት  አስተዋጾ በድጅቱ ና በስራ አስፈጻሚኮሚቴ ስም ምስጋና እናቀባለን!1

 

ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ

የዲሞክራሲያዊ ለውጥ በኢትዮጵያ የድጋፍ ድርጅት በኖርዌይ

The post የዲሞክራሲዊ ለውጥ በኢትዮጵያ ድጋፍ ድርጅት ኖርዌይ የአቶ አንዳርጋቸው ፅጌ 60ኛ አመት የልደት በአል በተሳካ ሁኔታ ተከናወነ appeared first on Zehabesha Amharic.

በሬ ሆይ ሳሩን አገኘሁ ብለህ ገደሉን ሳታይ… የግል አጭር አስተያየት

$
0
0

ከአበባዉ ላቀው (labebaw@gmail.com)

ሰሞኑን የኤርትራዉ “ፕሬዘዳንት” ኢሳያስ አፈወርቂ ለኢሳት ቴሊቪን ጋዜጠኞች መግለጫ ሰጥቷል። በዚህም እርሱ የተናገረዉን  ትርጉም ስሰማና አንዳንድ ወንድሞችና እህቶች ልባቸዉ ሲማልል ስሰማ በጣሙን አዘንሁ። ምክንያቱም እያንዳዱ ኢትዮጵያዊ  ይህን እብድ ጠንቅቆ ያውቀዋል የሚል ግምት ነበረኝ። ሆኖም ግን ግምቴ ትክክል አለመሆኑን የሰሞኑንን ግርግር በደንብ አሰረዳኝ።

ይህን ኢሳያስ የሚባል isayaበደ ዉሻ ኢትዮያን ነክሶ ዜጎቿን ለእብደት የዳረገ የሰይጣን ፍጡር አምነን ልባችን በተደጋጋሚ አይነሸዋረር! ብርሀኑ ነጋያራሱ ተልኮ ያለዉ ጸረ-ኢትዮጵያ ነዉ። 97ቱን የምርጫ ድል ከሕዝብ እጂ ተነጥቆ ለወያኔ ጀባ እንዲባል በጓሮ በር ከበረከት ጋር ስምምንነትያደረገ እኮ እርሱ ነዎ! ከምርጫ ሳምንት ቢኋላ ማክሰኞ ሊደረግ የነበረውን የሙት ከተማ አድማ ከበረከት ጋር ተስማምቶ እንዳይደረግ ያደረገእኮ እርሱ ነው! ያልሞተቸዉ ብርቱካን ሚዴቅሳ ትመሰክራለች። የብርሀኑን ከሀዲነት 16 የልደት ዘመኑ ጀምሮ በበረሃ ያደረገዉን የክህደትወንጀሎች ለማወቅ አሲምባ የነበሩ ሰዎችን ጠይቃችሁ ተረዱ።

ሕዝብ ሆይ ዝምብለህ ማንም አጭበርባሪ የነገረህን እያመንህ የመሪዉን ማንነትሳታጣራ እንደከበት አትነዳ! ጉዞው ወደገደል ነዉና! ይህ ሳያስ የሚባል እብድ እንኳን ለሚጠላት ኢትዮጵያና ሕዝቧ መልካም ሊያስብ ቀርቶየራሱንምሕዝቤየሚለወን የኤርትራ / ህዝብ መውጫና መገቢያ አሳጥቶታል። ሰሞኑን የአሜሪካው PBS African Programስለኤርትራ ህዝብ ስደትና መከራ የሚያስተላልፈው ዶክሜንታሪ በቂ ማስረጃ ነው። አባቶቻችንን፣ወንድሞቻችንን እና ዘመዶቻችንን እንክትአድርጎ የበላ ማነው? ባንዳ የባንዳ ልጅ ኢሳያስ አይደለምን?  በቀድሞ አለቆቹ (ጣልያንና እንግሊዝ እንዲሁም ተባባሪዎቻው) መሪነትኢትጵያን ሲደማ እና ሲያጠፋት የኖረ፣

ወያኔንን ከዉልደት ጀምሮ የፈጠረ፣ ከሃዲ ድርጅቶችን እንደነ ኦነግና አብኦነግ ያሉትን የፈጠረና ከወያኔ ጋር ባደረገዉ የዉሸት ጦርነት ከ70ሺ በላይ ወንድሞቻችንን የጨረሰ፤ ኢሳያስ አይደለምን?  አሁን ኢሳት ይህን ሰይጣን ቅዱስ አድርጎሊቃርብልን እና ልባችን ኢሳያስን ማመን ሲጀምር የእራሳችንን ጤንነት መመርመር ያስፈልጋል።  በተለይ በምዕራቡ አለም ውስጥ ያለን ዜጎች ዝምብሎ የተነገርንን ብቻ ሰምተን አሜን ብሎ መቀበሉ ያሳፍራል። ያለን እይታ ከሚኖረን ልምድ አንጻር ሰፋ ያለ ሊሆን ይገባዋል።

በየቀኑ የምናነባቸው እና የምንሰማቸዉ የአለም ዜናዎች፣ የፖለቲካ ትንታኔዎች ወዘተ የዕዉቀት አድማሳችንን ያሰፈላናል ብየ እገምታለሁ። ይህም እንደ ሰሞኑ ያለዉን የኢሳያስን ቀልድ አዘል ሌላ የ100 ዓመት የቤት ስራ ከልብ ሊገባን እና ልንቃወመው በተገባን ነበር። ዝምብሎ ማንም በሬድዮ ወይም ቴሌቪዥን የቀረበን ቃለመጠይቅም ሆነ ትንታኔ (ለዚያዉም የኢሳያስን)  የምናምን ከሆነ የበሬው እጣ እንዳይገጥመን እፈራለሁና  እንድናስተዉል እመክራለሁ። በዚህ ጉዳይ ላይ የጠለቀ ትንታኔ ለሚሰጡ ውድ የኢትዮጵያ ልጆች ጉድዩን በዚሁ ልተወው።

አክባሪያችሁ

አበባዉ

The post በሬ ሆይ ሳሩን አገኘሁ ብለህ ገደሉን ሳታይ… የግል አጭር አስተያየት appeared first on Zehabesha Amharic.

ቀና በል ይሉኛል–ወዴት ልበል ቀና

$
0
0

10989028_861493467244057_5753878234862957005_nቀና በል ይሉኛል– ወዴት ልበል ቀና
ከላይ ተደፍቶብኝ- አገር እንደቁና
ጣራው ባጡ ቀርቦኝ
በር አልባ ግድግዳ- እንደ ዝናር ከቦኝ
በጫጩት ጉልበቴ- እየተወራጨሁ
እንባየን ዘግኘ- ሽቅብ እየረጨሁ
ወደ አማልክት ብጮህ-ጠሎቴን አይሰሙት
በየት በኩል ኖሬ በየት በኩል ልሙት::
በምን ይገለጻል- የትውልዴ አበሣ
ከመንበርከክ ብዛት- መራመድ የረሣ
ያልፋል ተለጉሞ ያልፋል ተከርችሞ
የጉልበቱን ኮቴ- ምድር ላይ አትሞ::
ወፈፌ ቀን አልፎ- እብድ ቀን ሲመጣ
ማልቀስ አመጽ ሲሆን- በሸንጎ ሚያስቀጣ
እንባዬን የት ላርገው ወዴት ልሸሽገው?

ዞትር የሚስቁት፣
ወዴት ገቡ አበቦች
የሚፍለቀለቁት የታሉ ኮከቦች
ምን አጋይቶት ይሆን፤ ሰማይ የከሠለ
ምን ነካው ደመናው፤ ኩበት የመሠለ
አስፋልቱስ የት ሄደ
የተለጠለጠው
ወንዙስ ተሰደደ?
ድልድዩስ ምን ዋጠው
የት ተነነ ጫካው
የት መነነ ዋርካው
በለምለም ጣቶቹ፤
ሰማይ የሚነካው
ዳበስኩኝ ፈተሸኩኝ
መረመርሁኝ ካርታ
አገሬን አጣሁዋት፤
ባስቀመጥሁዋት ቦታ፡፡
ኢትዮጵያ እመ-መከራ
የግዜር መመራመሪያው የስቃይ ቤተ-ሙከራ
መውደቅማ ነበር ያባት
እንደ ያሬድ እስከ ሰባት
እንደ በላ ብላቴና ፣ የእንክርዳድ ሙልሙል እንጎቻ
የትውልዴ እጣ ፋንታ፣ መውድቅ መውድቅ መውድቅ ብቻ…

The post ቀና በል ይሉኛል– ወዴት ልበል ቀና appeared first on Zehabesha Amharic.

Hiber Radio: የህወሓት አስተዳደር የክርስትና ዕምነት ተከታዮችን ሀሳብን በነፃ የመግለፅ መብት እየተጻረረ መሆኑ.. ኢትዮጵያ የበርበራን ወደብ ለመጠቀም ማቀዷ…የኢ/ር ይልቃልና የዶ/ር መረራ ወቅታዊ ቃለምልልስ…አንዳርጋቸው እንዲፈቱ የሚጠይቅ ከ70 ሺህ በላይ ፊርማ ተሰባስቦ ለእንግሊዙ ጠ/ሚ/ር መሰጠቱ…የቬጋስ የደብረ ምህረት ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ አወዛጋቢው የሰበካ ጉባኤ ምርጫ ያስከተለው ክፍፍልና ሌሎችም

$
0
0

ጋዜጠኛ ሃብታሙ አሰፋ

ጋዜጠኛ ሃብታሙ አሰፋ


የህብር ሬዲዮ የካቲት 8 ቀን 2007 ፕሮግራም

እንኳን ለ78ኛው የየካቲት 12 የሰማእታት መታሰቢያ በዓል አደረሳችሁ

<...> ኢንጅነር ይልቃል ጌትነት የሰማያዊ ፓርቲ ሊቀመንበር ለህብር ሬዲዮ ከሰጡት ማብራሪያ (ሙሉውን ያዳምጡ)

በቬጋስ የደብረ ምህረት ቅዱስ ሚካኤል የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን አወዛጋቢው የሰበካ ጉባኤ ምርጫና ተከትሎት የመጣው ክፍፍል ስለ ጉዱዩ ከሰበካው ጉባኤ ዋና ፀሀፊ ከዶክተር አለባቸው ደሳለኝ የቤተክርስቲያኒቱ አስመራጭ ኮሚቴ ዋና ፀሀፊ አቶ መላኩ አምባቸው እና የሰበካው ጉባኤ ምርጫ ህጋዊ አይደለም ተቀባይነት የለውም ከሚሉ ወገኖች አቶ ዩሀንስ ዳኘው ጋር ያደረግነው ቃለ መጠይቅ

የየካቲት 12 መታሰቢያ (ልዩ ጥንቅር)

ቃለ መጠይቅ ከአቶ ኪዳኔ አለማየሁ ከአለም አቀፍ ሕብረት ለፍትሕ የኢትዮጵያ ጉዳይ ዋና ስራ አስኪያጅ ፋሺስት ጣሊያን በወገኖቻችን ላይ ያደረሰው ጭፍጨፋ በዓለም አቀፍ መድረክ ተገቢውን ትኩረት እንዲያገኝ የኢጣሊያ መንግስት ለኢትዮጵያ ተገቢውን ካሳ እንዲከፍል ስለሚያደርገው እንቅስቃሴ

<..> ዶ/ር መረራ ጉዲና የመድረክ ም/ሊቀመንበርና የውጭ ግንኙነት ሀላፊ ጋር ካደረግነው ቃለ መጠይቅ የተወሰደ(ሙሉውን ያዳምጡት)

ሌሎችም

ዜናዎቻችን

* ዕውቁ የነፃነት ታጋይ አቶ አንዳርጋቸው ፅጌ እንዲፈቱ የሚጠይቁ ከ70 ሺህ በላይ የተማፅኖ ፊርማዎች ለእንግሊዙ ጠቅላይ ሚኒስትር ተሰጡ

* ጠበቃቸው አዲስ አበባ ሄደው እንዲጎበኟቸው ለም/ቤት አባላት ተጠይቋል

* የኢህአዲግ አገዛዝ የደህንነትና የመከላከያ ባለስልጣናት ከኦብነግ ባለስልጣናት ጋር ሰሞኑን ኬኒያ ውስጥ መነጋገራቸው ተሰማ

ኢትዮጵያ የበርበራን ወደብ ለመጠቀም ማቀዷ ታወቀ

ዶ/ር መራራ ጉዲና ምርጫ ቦርድ በህገ ወጥ ምንገድ ዕጩዎቻቸውን እንዳይመዘገቡ እያደረገ መሆኑን ገለፁ

ህዝቡ ምርጫ እየሰረቅክ መግዛትህን አቁም ማለት አለበት ብለዋል

* ኢ/ር ይልቃል ጌትነት የሰማያዊ ዕጩዎች እንዳይመዘገቡ መታገዱ ምርጫ ቦርድ በሰማያዊ ላይ እርምጃ ለመውሰድ እየተንቀሳቀሰ መሆኑን ያሳያል አሉ

ትግሉ በተጠናከረ መንገድ ይቀጥላል

ቦርድ ሰማያዊን ዕጩዎችና ምልክቶች ሆነ ብሎ ይፋ አላደረገም እያገደም ነው ብለዋል

* የህውሃት ኢህዴግ አገዛዝ የክርስትና ዕምነት ተከታዮችን ሀሳብን በነፃ የመግለፅ መብት እየተፃረረ ነው አንድ የሀይማኖት ተቋም ወቀሳውን ገለፀ

ሌሎችም ዜናዎች አሉ

The post Hiber Radio: የህወሓት አስተዳደር የክርስትና ዕምነት ተከታዮችን ሀሳብን በነፃ የመግለፅ መብት እየተጻረረ መሆኑ.. ኢትዮጵያ የበርበራን ወደብ ለመጠቀም ማቀዷ… የኢ/ር ይልቃልና የዶ/ር መረራ ወቅታዊ ቃለምልልስ… አንዳርጋቸው እንዲፈቱ የሚጠይቅ ከ70 ሺህ በላይ ፊርማ ተሰባስቦ ለእንግሊዙ ጠ/ሚ/ር መሰጠቱ… የቬጋስ የደብረ ምህረት ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ አወዛጋቢው የሰበካ ጉባኤ ምርጫ ያስከተለው ክፍፍልና ሌሎችም appeared first on Zehabesha Amharic.


ተመስገን ደሳለኝ ምልክታችን ነው! –ከበድሉ ዋቅጅራ

$
0
0

ተመስገን ደሳለኝ ምልክታችን ነው፤ ልንሸፍነው ያልቻልነው ምልክት፡፡ ተመስገን የተከሰሰውና የተፈረደበት ከአሸባሪዎች ጋር ግንኙነት አለው ወይም ደግሞ አሸባሪ ነው ተብሎ አይደለም፤ የተከሰሰውም የሶስት አመት እስር የተፈረደበትም በጻፈው ጽሁፍ ነው፡፡ በመሆኑም ተመስገን ሀሳብን በነጻነት የመግለጽ ህገመንግስታዊ መብታችን ያለመከበር ምልክት ነው፡፡
Temesgen Desalegn behindbar
ተመስገን ጠንካራ ግለሰባዊ ሰብእናውንና ህገመንግስታዊ መብቱን በመጠቀም፣ ለዚህች ሀገርና ለህዝቦቿ ይበጃል ያለውን ሀሳብ ለመግለገልጽና በሰላማዊ መንገድ ለመሟገት አፍላ የወጣትነት እድሜው ያላጓጓው ዜጋ ነው፡፡ በመሆኑም ተመስገን የ‹መሬት ላራሹንና የብሄረሰቦችን መብት ጥያቄ አንግበው በነሳት ላመኑበት እንደታገሉት አይነት ወጣቶች ዛሬም ለመኖራቸው ምልክት ነው፡፡

ከሁሉም በላይ ተመስገን የዘመን ተሻጋሪው ኢትዮጵዊ አስተሳሰባችንና ስብእናችን አጋላጭ ምልክት ነው፡፡ በዘመነ ፊውዳሊዝም ለተገኘው ለውጥ (ትሩፋቱ በጎም ይሁን ክፉ) መስዋእትነት የከፈሉት ጥቂቶች ናቸው፡፡ በደርግ አብዮታዊ አገዛዝ ዘመንም የታሰሩት፣ ተገድለው የተጣሉት፣ ለትግል የወየኑት፣ የተሰደዱት ጥቂቶች ናቸው፡፡ አሁንም ከዚሁ የተለየ አይደለም፤ ስለህዝባችንና ሀገራችን፣ ስለፖለቲካዊው አስተዳደራችን ያገባናል ብለው በድፍረት መንግስትን የሚሞግቱት ጥቂቶች ናቸው፡፡ በሶስቱም ዘመን በአጋጣሚው ተጠቅመው ሀገራዊና ህዝባዊ ጥቅምን፣ በአንድ እንጀራ አፉን ለሚዘጋ ወስፋታቸው ጩኸትና በቃኝ ለማያውቅ ፍትወተ-ንዋይ ማርኪያ የተጠቀሙበት በርካቶች ናቸው፡፡ አብዛኛው ህዝብ ግን በገዢዎቹ የጭካኔ ድንኳን ውስጥ በፍርሀት ተደቅድቆ ‹‹በአያገባኝም›› እንዳላዘነ አለ፡፡ ይህ ህዝብ ስለልጁ መረሸን አልጠየቀም፤ አላለቀሰም፡፡ በገዢዎቹ የሚጣሉበትን አዋጆች ይቆጥራል እንጂ፣ በአዋጆቹ ስለሚያጣው መብቱ ወይም ስለሚያጎናጽፉት ትሩፋት አይጠይቅም፡፡ ይህ ህዝብ እያጨበጨበ የሚፈጥራቸውን ተሟጋቾቹን (ጀግኖቹን) እራሱን እየነቀነቀ ወደ እስር ቤት፣እያለቀሰ ወደ ቀብር ከመሸኘት በቀር ‹‹ለምን?›› ብሎ አይጠይቅም፡፡ በመሆኑም ተመስገንና ሌሎች ሀሳባቸውን በሰላማዊ መንገድ ሲገልጹ፣ ለእስርና ለስደት የተዳረጉ ዜጎች፣ የዚህ ከዘመን ጋር እየሰለጠነና እየዳበረ የመጣ ጸያፍ ኢትዮጵያዊ ስብእና አሉታዊ ምልክቶች ናቸው፡፡

The post ተመስገን ደሳለኝ ምልክታችን ነው! – ከበድሉ ዋቅጅራ appeared first on Zehabesha Amharic.

ሌንጮ ለታ፤ ኦኤምኤን ፤ አባዱላ ገመዳ እና የሞራል ኪሳራ –እንደ ተጨማሪ ማብራሪያ

$
0
0

ከታምራት ነገራ

(የቀድሞው አዲስ ነገር ጋዜጣ ጋዜጠኛ)

ይህ ፅሁፍ በክፍል አንድ ( ኦኤምኤን ፤ አባዱላ ገመዳእና የሞራል ኪሳራ) በሚል ርስዕስ ላይ ባነሳኋቸውን አንዳነድ ነጥቦች ላይ ተጨማሪ ማብራሪያ ለመስጠት ይሞክራል፡፡ በክፍል አንድ ጽሁፍ በጥቂቱ ኦኤምኤን እንደሚዲያ ተጠያቂነቱ ለአንድ ቡድን ወይንም ፓርቲ ሳይሆን ለኦሮሞ ብሔርተኝነት እንደሆነ፤ ኦህዴድ በዋነኛነት የሚንቀሳቀስበት የፖለቲካ ኢኮኖሚ ስሌት የድኾበል ( እየዳኸ የሚበላ Bottom Feeder) ፖለቲካዊ ኢኮኖሚ ስሌት አንድሆነ፤ ኦኤሜንን እና ኦህዴድን የሚያገናኛቸው እናም አንዱ ሌላውን እንዲሸከመው ያደረገው የኦሮሞ ብሔርተኝነት ውስጥ የተፈጠረው የሞራል ቀውስ እንደሆነ፤ የኦሮሞ ብሔርተኝነት ውስጥ የሞራል ቀውስ የሚመነጨው ከወቅተዊው የኦሮሞ ብሔርተኝነት (Contemporary Oromo Nationalism) በጥቂቱም ቢሆን ለማሳየት ሞክሬአለው፡፡
lencho leta
ይህም ሆኖ በጽሁፉ በሚገባ ያላደማኋቸው የተወሰኑ ወሳኝ ነጥቦች ታይተውኛል አንባቢዎችም አንዳንድ ተጓዳኝ ጥያቄዎችን በቀጥታም ሆነ በግል መልዕክት አቅርበዋል፡፡ እኔ በጽሁፉ ላይ ያየኋቸውን ነጥቦች እና የተነሱትን ጥያቄዎች በጥቅሉ ሳስቀምጣቸው፤

አንደኛ፤ ፅሁፉ የሞራል ኪሳራ ወይንም የሞራል ቀውስ የሚለውን ጽንሰ ሀሳብ በተገቢው አላብራራም፡፡ በተጨማሪም የጽሁፉ መነሻ ባረደገው ክስተት (የኦኤም ኤን ጋዜጠኞች ከአባዱላ ጋር ምግብ መቋደስ ጋር) የሞራል ክስረት ምን አይነት ግኑኝነነት እንዳለው በሚገባ ሳያሳይ በደፈናው ያልፈዋል፡፡
ሁለተኛ፤ ፅሁፉ በኦሮሞ ብሔርተኝነት ውስጥ ስላለው የሞራል ቀውስ ሲተነትን በኢትዮጵያ ብሔርተኞች ዘንድ መሰረታዊ ስለሚባሉት እንኳን የኦሮሞ ጥያቄዎች ያለው ክህደት አልዳሰሰም፡፡ የኢትዮጵያ ብሄርተኞች ስለኦሮሞ ጥያቄ የሚያሳዩት ተራ ድንቁርና ለኦሮሞ ብሔርተኞች ጽንፈኝነት በቀጥታ ስላበረከተው አስተዋፅኦ እናም በኦሮሞ ወቅታዊ ብሔርተኝነት ውስጥ ለምናየው የሞራል ቀውስ ስለበረከተው አስተዋጽኦ አልተብራራም፡፡

ሶስተኛ፤ ፅሁፉ ስለኦህዴድ ፓለቲካዊ እና ኢኮኖሚያዊ ስሌት ሲተነትን እነ ኦኤሜንም ሆኑ በርካታ የኦሮሞ ብሄርተኛ ልሂቃኖች የሚሰብኩት እና የሚከተሉት የፖለተካዊ ስሌት እንዴት አድርጎ ከኦህዴድ አጠገብ እንዳስቀመጣቸው ኦህዴድም እነኦኤምኤንን ለራሱ ግብ እንዴት እነደሚጠቀምባቸው ፍንትው አድርጎ አላሳየም።

አራተኛ ፤ፅሁፉ በአሁኑ ወቅት በኦሮሞ ፖለተካ ውስጥ ካለው እንቅስቃሴ በተለይም እነ ሌንጮ ለታን መሰል ግንባር ቀደም የኦሮሞ ብሔርተኞች ወደ አገርቤት መመለስን አስመልክቶ ምንም ያለው ነገር አልነበረም፡፡ የእነ ሌንጮ ለታ እርምጃ በምን አይነት ስሌት ላይ ተመሰረተ ሊሆን ይችላል? የእነ ሌንጮ ለታ እርምጃ በኦሮሞ ብሔርተኝነት ውስጥ የተፈጠረውን ሞራል ቀውስ ከመረዳት እናም መፍትሄ ለመስጠት ከመሞከር አንጻር እንዴት ሊታይ ይችላል? ይህ ጽሁፍ እነዚህን ነጥቦች እና ጥያቄዎች ለመዳሰስ ይሞክራል፡፡

የሞራል ወይንስ የፖለቲካ ጥያቄ

በየትኛውም የፖለቲካ እንቅስቃሴ ውስጥ የሞራል ጥያቄን እና የፖለቲካ ጥያቄን አመሰረታቸውን፤ ልዩነታቸውን፤ መስመራቸው ደግሞ የትጋር እንደሚተላለፉ ማወቅ እጅግ ወሳኝ የቤት ስራ ነው፡፡ ምክንያቱም በፖለቲካዊ ጉዞ ወስጥ የሞራል እና የፖለቲካ ጥያቄ ግጭት ፈፅሞውንም አይቀርም ፤ ለአንድ ሰከንድ አንኳን አይቋረጥም ለመቼውም ሙሉ ለሙሉ አርኪ መልስም አያገኝም፡፡

አንድዳንድ አጋጣሚዎች የሚያቀርቧቸው አማራጮች የፖለቲካ ፍላጎቶች እና ጥቅሞቻችን ከሞራል መርሆዎቻችን አስበልጠን ለፖለቲካዊ ጥቅማችን እንድናደላ ሊያስገድዱን ይችላሉ፡፡ በተመሳሳይ መልክም አንዳንድ አጋጣሚዎች ለሞራል ግዴታዎቻችን በመታዘዝ ከፖለቲካዊ ፍላጎቶቻችን እና ጥቅማችን በልጦብን ፓለቲካዊ ጥቅማችንን እርግፍ አድርገን እንድንጥል ሊያስገድደንም ይችላል፡፡

ፖለቲካዊ ጉዞን የሚያወሳስበው አንድ ነገር ለፖለቲካዊ ጥቅም ስንል የሞራል መርሀችንን ለመጨፍለቅ ስንወስን የወሰድነው እርምጃ መልሶ የፖለቲካዊ ትቅማችንን እጅጉን ሊጎዳው መቻሉ ነው፡፡ ልክ በተመሳሳይ መልኩ የሞራል ጥቅማችንን ከፖለቲካ ጥቅማችን አስበልጠን የወሰድነው እርምጃ በራሳችንም በዓለም ፊት ያለንን የሞራል ቁመና ለመደምሰስ መቻሉ ነው፡፡ በብዙ ጊዜ እነዚህን ውስብስበሰ እና አጣብቂኝ ውሳኔዎች እንድንወስድ የምንገደደው በአጭር ጊዜ ውስጥ እና በተወሰነ መረጃ ላይ ብቻ በመመስረት ሊሆን ሆናል፡፡
እነዚህን ምርጫዎች በትክክል እና በተቻለ አቅም በተማጠነ መልኩ ለመውሰድ ግን የሚያስፈልገን በደመነፍስ መደንበር፤ የሰለቹ መፈክሮችን በጩኸት መልሶ መላልሶ መድገም ሳይሆን የፖለተካ ጥያቄን ከሞራል ጥያቄ በሚገባ ለይቶ ለማወቅ መታገል ነው፡፡

የኦሮሞ ጥያቄ የሞራል ወይንስ የፖለቲካ ጥያቄ ?

የኦሮሞ ጥያቄ የሞራል ጥያቄ ነው ወይንስ የፖለቲካ ለሚለው ጥያቄ መልስ ለማቅረብ ከመሞከር በፊት የኦሮሞ ጥያቄ እራሱ ምንድን ነው ከሚል ጥያቄ ጋር እንጋፈጣል፡፡ይህ ጥያቄ እራሱ ሰፊ እናም ጥልቅ የጥናት ፕሮጀክት ነው፡፡ ነገር ግን አሁን እየተወያየንበት ላለው ርዕሰ ጉዳይ አንድ ጥያቄ እንዴት የፖለቲካ እና የሞራል ጥያቄ መልክ እንደሚኖረው፤ ምን አይነት ጥያቄ የሞራል ጥያቄ ሊባል አንደሚችል ምን አይነት ጥያቄ ደግሞ የፖለቲካ ጥያቄ ሊባል እነደሚገባው መወያያ ይሆነናል እላሁ፡፡

የኦሮሞ ጥያቄ፤ የሲዳማ ጥያቄ፤ የአፋር ጥያቄ ወዘተ ስንል በመጀመሪያ ስለአንድ ህዝብ ጥያቄ እተወያየን ነው፡፡ ስለዚህ የኦሮሞ ጥያቄ ስንል የኦሮሞ ሕዝብ ጥያቄ ነው፡፡ እዚህ ላይ መቆም ግን በቂ አይሆንም አይደለምም፡፡ የሕዝብ ጥያቄ ስንል መቼም አባላት የሆኑት ሚሊዮኖች ሁሉ በአንድ ቀን ተሰብስበው በአደባባይ የሚያቀርቡት ጥያቄ ማለታችን አይደለም፡፡ አንደኛ በረጅም ጊዜ ውስጥ እና ውስብስብ ፖለቲካዊ ባሕላዊ ኢኮኖሚያዊ ሂደቶች ውስጥ አልፎ የሚገነባ ጥያቄ ነው፡፡ ሁለተኛ እና በዋነኛነት በአንድ ሕዝብ ጥያቄ ዙሪያ እጅጉን ወሳኝ ተዋናይዮች ልሒቃን (Elites )ናቸው፡፡

የአንድ ሕዝብ ልሒቃን የሕዝቡ ጥያቄ ምን መሆን እንዳለበት ይወስናሉ፡፡ የተቀረጸውን ጥያቄ በሕዝባቸው መካከል ያስፋፋሉ፡፡ በጥያቄው ዙሪያም ሕዝባቸውን ያደራጃሉ ያነቃቃሉ፡፡ ይህን የሚያደርጉት ለሕዝባቸው ከመቆርሮርም ለግላቸው ፖለቲካዊ እና ኢኮኖሚ ጥቅም ለማግኘትም ሲሉ ነው፡፡ ስለዚሕ የኦሮሞ ጥያቄ ስንል፤ የኦሮሞ ልሒቃን ለህዝባቸው ከመቆርቆር እናም የግል ፖለቲካዊ እና ኢኮኖሚያዊ ጥቅማቸውን ለማስፈፀም የሚቀርፁት የሚያስፋፉት ብዙሃን ኦሮሞችን ለማደራጀት የሚጠቀሙበት ጥያቄ ነው ብንል ከእውነታው እምብዛም አንርቅም፡፡ የአንድ ሕዝብ ጥያቄ መቀረጽ እና መስፋፋት በዚያ ሕዝብ ውስጥ የሚኖረውን የብሔራዊ ስሜት ይጭራል ይቀሰቅሳል ያቀጣጥላል፡፡ በዚህ የተነሳ የሕዝብ ጥያቄ፤ ብሔርተኝነት እና ልሂቃን እጅግ ወሳኝ የሆነ ትስስሮሽ አላቸው፡፡

የአንድ ሕዝብ ልሂቃን ሕዝባቸውን ወክለው እንዲነሱ የሚያደርጓቸው ወሳኝ ነገሮች አንደኛው ልሂቃኑ በሕዝባችን ላይ ጭቆና አለ ብለው ማመናቸው ነው፡፡ ልሂቃኑ አለ የሚሉት ጭቆና ኖረም አልኖረም የህዝቡ ልሂቃን ጭቆና አለ ብለዋል እዚህ ላይ መነታረክ ትርጉም የለውም፡፡ ጂኒው ከሳጥኑ አምልጦ ወጥቷል፤ ጥያቄውም ተጭሯል፡፡ ልሂቃንን በሕዝብ ስም ሆ ብለው እንዲነሱ የሚያደርገው ሁለተኛው መስፈርት የልሂቃኑን ፖለቲካዊ እና ኢኮኖሚያዊ ጥማት በሚገባ መልኩ የማያረካ ስርአት መኖሩ ነው፡፡

ስለሕዝብ ጥያቄ ልሂቃን በሕዝብ ጥያቄ ዙሪያ ስለሚኖራቸው ሚና እና የሕዝብ ጥያቄ ስለሚመሰረትበት ፖለቲካዊ እና ኢኮኖሚያዊ አውድ ይህን ያህል ከተነጋገርን ስለኦሮሞ ሕዝብ ጥያቄ ምንነት፤ ፖለቲካዊ እና ሞራላዊ ይዘቱ ጀምረነው ወደነበረው ውይይት አንመለስ፡፡ እስቲ ውይይታችንንም በአሁኑ ወቅትም ሆነ በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ የኦሮሞ ልሂቃን ስለኦሮሞ እንዲቆሮቆሩ የሚያሳምናቸው ፤ የኦሮሞ ሕዝብ ከሌላው የኢትዮጵያ ሕዝብ ጋርም ሆነ ለብቻው በኦሮሞነቱ ተለይቶ ተበድሏል እንዲሉ የሚያስችላቸው ጭቆና ነበር አልነበረም የሚንለውን ጥያቄ በመቃኘት እንጀምር፡፡

ለዚህ ጥያቄ በኦሮሞ ሕዝብ ላይ የተለየ ጭቆና አልደረሰም የሚል መልስ የሚሰጡ ሰዎች መልሳቸውም ሆነ መልሳቸውን ለማስደገፍ የመያቀርቧቸው ማስረጃዎቸው ምን ያህል ትርጉም የለሽ እነደሆኑ ቢረዱ ደስ ባለኝ፡፡ የኦሮሞ ልሂቃን ኦሮሞን ከሌላው ሕዝብ በተለየ መልኩ ተጨቁኖአል ተበድሏል የምንልበት አሳማኝ ምክንያት አለን ካሉ በቃ አለቀ ደቀቀ አሳማኝ ምክንያት አለ፡፡ አንደው አልነበረም እንኳ ብንል ልክ እነደ ልብ ወለድ ከምንም ውስጥ ይፈጥሩታል፡፡ ልሂቃንነታቸው ለዚህ ቀን ካልዋለ ለመቼ ?
aba dula
የታሪክን ክርክር ለጊዜው ጋብ እናድርገው እና በዛሪቷ የኢትዮጵያ ስርአት ውስጥ ማን ኅሊናው ንጹ የሆነ ሰው አፉን ሞልቶ ኦሮሞ በኦሮሞነቱ እየታደነ እተገደለ ከመሬቱ እየተነቀለ አይደለም ይላል ? ዛሬ በኦሮሞ ላይ እየደረሰ ያለውን ሰቆቃ ለማወቅ የኦሮሞ ልሂቅም መሆን ኦሮሞ መሆን አያስፈልግም፡፡ ስለዘንድሮ የኦሮሞ ሰቆቃ አሳሳቢነት ስዬ አብረሃ የእስርቤቱ ቋንቋ ኦሮምኛ ሆኑአል ካለው የበለጠ ገላጭ ቃል ማግኘት ይከብዳል፡፡ ይህን ያለው ስዬ ግን ኦሮሞም አይደለም እንደውም የዘንድሮው ስርአት ዋነኛ አርክቴክትም ነበር፡፡

ስለዚህ የኦሮሞ ጥያቄ ስንል ሌላው ሁሉ ቢቀር በተገቢው ፍትህ የመኖር፤ ከቤት በሰላም ወጥቶ በሰላም የመመለስን የሚያክል እጅግ መሰረታዊ የሞራል ጥያቄ ማለታችን ነው፡፡ ይህንን በሰላም የመኖር ጥያቄ አንዴት መልስ እናግኝነለት? በብሔር እና ቋንቋ ላይ በተመሰረተ ፌደራሊዝም ወይንስ በአሃዳዊ ስርአት በማለት መጀመሪያ ላስቀመጥነው የሞራል ጥያቄ መልስ ማቅረቢያ ሌሎች የመዋቅራዊ ጥያቄዎችን ስንጋፈጥ የሞራል ጥያቄው ወደ ፖለቲካ ጥያቄ ገጹን ይቀይራል፡፡

የሞራል ጥያቄዎች በአብዛኛው እንዲህ እና እንዲያ መሆን አለበት እንዲህ እና እንዲያ መደረግ አለበት (What ought to be) የሚል ጫና ያዝላሉ፡፡ የሞራል ጥያቄዎች ዓለምን ሲያዩ ምን አንደጎደለ ፤ ምን መስተካከል እንደለበት ለማሳየት ይጥራሉ፡፡ የፖለቲካ ጥያቄዎች ደግሞ በአብዛኛው አሁን ያለው ስርአት የሚንቀሳቀሰው እንዴት ነው ስርአቱን ምን አይነት ሰዎች ያስተዳድሩታል በየት አቅጣጫ ብንሄድ ምን አይነት ውጤት ያስገኙልናል የሚሉ ሲሆን ዓለምን በአብዛኛው ምን መሆን አንዳለበት ለማሳት ከመጣር ይልቅ ዓለም ምን እነደሚመስል እንዴት እንደሚንቀሳቃስ በማሳየት (What is ) ላይ ያተኩራሉ፡፡
ወደ ሌላ ነጥብ ከመሸጋገራችን በፊ በኦሮሞ ብሔርተኝነት ጽንፈኝነት (Radicalization) ላይ የኢትዮጵያ ብሔርተኞች ያበረከቱት አስተዋጽኦን ማንሳት ተገቢ ይሆናል፡፡ የኦሮሞ ብሔርተኝነት ከውልደቱ ጀምሮ እስከአሁን ድረስ ከኦሮሞ ልሂቃን ለኢትዮጵያ ብሔርተኝነት የተሰጠ ምላሽ (Reaction) ነው ብሎ መግለጽ ይቻላል፡፡ ሁለቱ የብሔርተኛ ካምፖች እንዴት አንደሚመጋገቡ የኦሮሞ ፈርስትን ንቅናቄ ያህል ማሳያ ያለ አይመስለኝም፡፡

የኦሮሞ ፈርስት እንቅስቃሴ በዋነኛነት የተወለደው ጃዋር መሀመድ እና መሀመድ አዴሞ ከአልጀዚራ ቲቪ ጋር በአደረጉት ውይይት ወቅት ጃዋር ለቀረበለት ጥያቄ እነደማለፊያ በሰጠው መልስ ላይ ነው፡፡ የኢትዮጵያ ብሔርተኞች በወቅቱ ለጃዋር እና ለሰጠው መልስ ያሳዩት ቁጣ “ሰዉ አብዷልን? ” የሚያስብል ነበር፡፡ ጃዋር በወቅቱ የተናገረው አዲስ ወንጌል አልነበረም፡፡ ለማንኛውም የፖለቲካ እና ማሕበራዊ ጉዳይ ተከታታዮች እነጃዋር ከዛ በኋላ የወሰዱት ወደ ሕዛባቸው ጉያ የማፈግፈግ ምላሽ በጣም የሚጠበቅ ነበር፡፡ ይህም ሆኖ እኔ ግን የኦሮሞ ብሔርተኝነት መክረር የኦሮሞ ልሒቃንን የበለጠ የፖለቲካዊ አቅም አሳጥቷል ለ ኦህዴድም መጠቀሚያ አንዲሆኑ አድርጓል ባይ ነኝ፡፡

የኦሮሞ ብሔርተኝነት እጅጉን መክረር እንዴት አድርጎ ለኦህዴድ እንደሚያገለግል ወደበኋላ እመጣበታለሁ፡፡ ለአሁኑ ግን የኦሮሞ ልሒቃን እራሳቸውን ከ መላሽነት ይዞታ (Reactionary Mode ) እንዴት እንደሚያነሱ ቢያስቡ እጅጉን ደስ ይለኛል፡፡ የእራስን እድል በራስ ስለመወሰን የሚያወራ ሰው ስሜቱን፤ ፍላጎቱን፤ አጀንዳውን፤ ውሳኔውን ሌሎች ስለእሱ ባላቸው እይታ፤ እና አመለካከት እርምጃ ላይ የሚመሰርት ከሆነ በምን መሰረት ላይ ቆሞ ስለ የእራስን እድል በእራስ ስለመወሰን ያወራል? የእራሱን ትናንት ዛሬ እና ነገ ከማንም ጋር ሳያነጻጽር መገንባት ያልቻለን አንዴት ስለ እራስ እድል መወሰን ሲሰብከኝ አምነዋለሁኝ?
ኦሮሞ የራሱን እድል የሚወሰወን ሕዝብ እንዲሆን የሚፈልግ የኦሮሞ ልሂቅ በመጀመሪያ በዓለም ላይ ከኦሮሞ ውጪ ሰው የሌለ እስኪመስል ድረስ ከምንም ነገር ጋር ከማንም ጋር እራሱን ሳያወዳድር በማንነቱ ላይ ብቻ ቆሞ ያናግረኝ፡፡ ኦሮሞነቱን አማራ እንዲህ ስላለኝ ትግሬ እንዲህ ስላሰበ ከሚል መሰረት የሚመነጭ ትንታኔም ሆነ ተረት ላይ መስርቶ አይስበከኝ፡፡ ሰማይ እና ምድር ከመፈጠሩ በፊት እኔ ታምራት ነገራ ኦሮሞ ነበርኩኝ፡፡ ሰማይ እና ምድር ካለፉም በኋላ እኔ ታምራት የኦሮሞ ልጅ ነኝ፡፡ የእኔ ኦሮሞነት የሚጀምረው አማራን ያየዩት ቀን ትግሬን ያነገርኩት እለት ሶማሌን የነካሁት ሰሞን አይደለም፡፡ እኔ ነበርኩ፤ እኔ ነኝ እኔ ለዘላም እኖራለሁ! ይሄን አይነት ዩኒቨርስን የሚያጨናንቅ ፈጣሪን የሚፈታተ ጥጋበኝነት የተሞላ ኦሮሞ ካለ እሱ ያናግረኝ፡፡ ኦሮሞነቱን አማራ ስለሱ በፃፋው ላይ ትግሬ ስለእሱ ባወራው ላይ የሚመሰርት እሱ እና እኔ አንተዋወቅም፡፡

የኦኤምኤን አባዱላ ጣጣ

ለወያኔ ስርአት የኦሮሞ ልጆችን አዳኙ ማነው? የኦሮሞ ልጆች በቤታቸው ያወሩትን ተርጉሞ ለወያኔ ነግሮ የሚያሳስረው ማነው ? የታሰሩትን የኦሮሞ ልጆች በኦሮምኛ የሚመረምረው የሚገርፈው ማነው ? አሳሳሪው እናም ገዳዩያው አባዱላ ገመዳ የሚያንቀሳቅሰው የኦህዴድ መዋቅር ነው፡፡ አባዱላ ገመዳ ጋር የኦኤምኤን ጋዜጠኖች ቢዴና የተቋደሱት ይህን እያወቅ እነደሆነ ብንገምት ስህተት አይሆንብንም፡፡ ይህ እንዴት የሞራል ቀውስ ያስከትላል?የሞራል ቀውስ መነሻ የሚጀምረው አንድ ሰው አምነዋለሁ እናገረዋለሁ እተገብረዋለሁ በሚለው ቃል ሳይገኝ ሲቀር ነው፡፡
ባለፈው የፈረንጆቹ ዓመት የአዲስ አበባን ማስተር ፕላን በመቃወም በመላው ኦሮሚያ በተነሳው ብጥብጥ ከወለጋ እስከሀረር የኦሮሞ ልጆቸችን ሲያድን ሲያስር ሲገድል የነበረው ማነው ኦኤምኤን በወቅቱ በሰፊው የዘገበው ኦሮሞ ፕሮቴስት የተሰኘው ዘመቻ ያነጣጠረው በኦሮሞ ገዳዩች ላይ ከሆነ ከአባዱላ እና ኦህዴድ በላይ የኦሮሞ ገዳይ ማን አለ? ለዚህ የኦኤምኤን እና የአባዱላ ቀውስ ከሌላው ሰው ይልቅ ሰፊ መልስ የሰጠው ከኦኤምኤን መስራቾቹ አንዱ የሆነው ጃዋር መሀመድ ነው፡፡ በግል የፌስቡክ ገፁ ላይ ግልገል ነፍጠኞችን ምንድነው የሚያንጫጫቸው? በሚል ርእስ ካቀረበው ጽሁፍ ይህን ጉዳይ አስመልክቶ ያቀረበውን ክፍል ልጥቀስ

“ታዲያ ዛሬ የኦሮሞ ጋዜጠኖች (ልብ በሉ የ ፖሊቲካ መሪዎች አይደሉም) ሙያዊ ግዴታቸውን ለመወጣት ከ አባዱላ ጋር ቢገናኙ ይህን ሁሉ ጩሀት ምን ቀሰቀሰው? መልሱ ቀላለ ነው። ለግልገል ነፍጠኞች እና ወያኔዎች ከምንም እና ማንም በላይ የሚያስፈራ ነገር ቢኖር እርስ በርሳቸው ጠላቶች ናቸው ብለው የሚጥብቋቸው ኦሮሞዎች አብረው መታየት ነው። እንደነሱ ፍላጎት ኦሮሞ በቡድን ተከፋፍሎ ሁሌም አንዱ አንዱን እያብተለተለ፣ አንዱ የኦሮሞ ቡድን ከነሱ ጋር አብሮ ሌላ ቡድን ውስጥ ያሉ እህቶች እና ወንድሞቹን እየዘረጠጠ እራሱንም እያዋረደ ባዕዳንን እያስፈነደቀ ቅሌት ሲሸከም ነው። እነሱ ማየት የሚፈልጉት እና የለመዱት የኦሮሞ ልጆች በመኢሶን፣ እጭአት፣ ኦነግ፣ ኦህዴድ፣ ኦዲፍ፣ ኦፍሲ … የ ዳዉድ ኢብሳ ኦነግ፣ የከማል ገልችሁ ኦነግ፣ የገላሳ ዲልቦ ኦነግ እንዲሁም የ ሌንጮ ለታ ቡድን ፣ የመረራ ጉዲና፣ የቡልቻ ደምቅሳ ተብሎ ተደርድሮ እየትኳረፈ፤ ከቻለም እየተታኮሰ ሲፋጭ ማየት ነው። እንደነሱ ፍላጎት አባዱላ አብዲ ፊጤን በታንክ ደምስሶ ሲሸልል ወይንም አብዲ ፊጤ አባዱላን በ አስቀያሚ ስድብ ዘርጥጦት ሲያዋርደው አይተው ሁለቱንም ለ mutual self destruction ማበረታታት ነው።”

በመጀመሪያ እንደጃዋር ትንተና ከሆነ በአባዱላ እና ኦኤምኤን ግኑኝነነት የተንጫጩት በሙሉ ግልገል ነፍጠኞች ናቸው፡፡ በአባዱላ እና ኦኤሜን ግኑኝነት የተቆጡትን ሁሉ ግልገል ነፍጠኞች ብሎ መፈረጅ በውስጡ እጅግ አሳዛኝ ስህተት አዝሏል፡፡ እኔም ሆንኩኝ ሌሎች ኢትዮጵያዊ ብሔርተኛ የሆንን ኦሮሞዎች መቼም ግልገል ይሁን ኮርማ ነፍጠኛ፤ ጎበና ይሁን house nigger ተብሎ መፈረጅ ፤መረገም መሰደብ ምንም አይመስለንም፡፡ ነገር ግን ከእነጃዋር ጋር ገንዘባቸውን፤ ጊዜአቸውን፤ እውቀታቸው አዋጥተው ኦኤምኤንን ያዋቀሩ አሁንም ኦኤምኤንን እያገዙ ያሉ ነገር ግን በአባዱላ እና ኦኤምኤን ጋዜጠኞች ግኑንኝት የተቆጡትን ኦሮሞ ብሔርተኞችም ከእኛ ጋር ደርቦ ወምቀጡ ለእነሱም ለተነሳውም ጥያቄ የጃዋር ገለጻ ፍትህ ይጎድለዋል እላለሁ፡፡ ጥያቄውን ለማጣጣል ከመጣር ጥያቄውን በድፍረት እና በእውነት መጋፈጥ ሳይሻል አይቀርም፡፡

በመቀጠል ከላይ እነዳስቀመጥኩት በኦኤምኤንም እና አባዱላ ቢዴና መቋደስ በርካታ ሰዎች በዋነኛነት የተቆጡት ለምን የኦኤምኤን ጋዜጠኞች በቃላቸው አልተገኙም ? እነዚህ ጋዜጠኞች የኦሮሞ ወቅታዊ ሰቆቃ ያንገበግበናል የሚሉ ሰዎች አይደሉምን ?የሚል ትያቄ ነው፡፡ የእነዚህ ሰዎች ጥያቄ የተመሰረተው በምናባቸው ሳይሆን የኦኤምኤን ጋዜጠኞች ላይ በታየው መሰረታዊ የእምነት ንግግር እና ተግባር ግጭት ነው፡፡ ለዚህ የሞራል ክስረት ጣጣ ጃዋር ያቀረበው ምልከታ የኦኤምኤን እና የኣባዱላ ግኑኝነት የተቆጣነው ሰዎች የቁጣችን ምንጭ ኦሮሞ አንድ እንዲሆን ማየት ስለማንፈልግ ነው፡፡ ይሄ የአንድነት ጥሪ (አንድነቱ በኦሮሞዎች መካከል ብቻ ነው ለጊዜው) በውስጡ ብዙ ትልልቅ ስንጥቆች አሉበት፡፡

አንደኛ ኦኤምኤን ከምር ከአባዱላ ጋር መታየት ፈጽሞ ካላሳፈረው የባለሙያነት ግዴታቸው ሊወጡ ሲሉ እራት ተጋብዘው ምናመን የሚል ሌላ ሀተታ ምክንያት ማቅረብ አያስፈልግም፡፡ በቃ ልክ ኢሳት ለሻቢያ እና ኢሳያስ አፈወርቂ እንደሚያሸረግደው ከዛ ደግሞ አይኑን በጨው አጥቦ ያለእኔ ኢትዮጵያ አንድነት ጠባቂ የለም እነደሚለው ኦኤምኤንም አይኑን በጨው አጥቦ የለምንም እፈረት ፊንፊኔ ገብቶ ላይቭ ዜና ይዘግብልን፡፡ ከዛም ደግሞ ያለ እኔ የኦሮሞ ድምጽ የሚያሰማ የለም ይበለን፡፡ ኢትዮጵያ አንደው መደነባበር አዲስ አይደል፡፡

ሁለተኛ እነጃዋር እነደሚሉን በኦሮሞ ልጆች መካከል ያለውን የአይዲዮሎጂ ልዩነት ተሻግሮ አባዱላ ገመዳን ለመሸከም የሚችል ትከሻ ካለ ወይንም አንዲህ አይነት የአይዲዮሎጂ ትከሻ መኖር ካለበት ለምን አባዱላ ገመደን በመሸከም ላይ እንቆማለን ? በዚህኛው ፌክ አባዱላ ላይ ከመቆም ወደኋላም ከታሪክ ራቅ ብለን የራሱ ጦር ከነበረው የፈረሱ እስትንፋስ ብቻ ተራራራን ከሚንጠው እውነተኛው አባዱላ እስከራስ ጎበና ዳጬ ድረስ ሄደን የኦሮሞን ታሪክ ለምን አንሸከምም? እነጃዋር አባዱላ ዛሬ እያፈሰሰ ያለው ኦሮሞ ደም ራስ ጎበና ዳጬ አፍሶታል ከሚሉት በምን እነደሚለይ እስቲ ይንገሩን፡፡

ሶስተኛ ኦሮሞ አንድ ነው ኦሮሞ አልተከፋፈለም ብሎ ሆ ማለት ለጊዜው የተወሰኑ ሰዎችን ያሰባስብ እነደሆነ እንጂ ኦሮሞ ባይከፈል ኖሮማ እነ አባዱላ አሳልፈው ባልገበሩን እኛም በአገራችን በኖርን፡፡ ከመካከላችን ለመጥረቢያው መያዣ በመሆን እያስጨፈጨፉን ያሉትን ወንድሞቻችን እና እህቶቻችችን እኛም አወቅናቸው ዓለም አውቋቸው የአደባባዩን ሚስጥር ለመሸፋፈን ምን አቻኮለን? ጃዋር እነደሚለን በኦሮሞ መካከከል አለመግባበት አንዳለ ለማወቅ “አባዱላ አብዲ ፊጤን በታንክ ደምስሶ ሲሸልል ወይንም አብዲ ፊጤ አባዱላን በ አስቀያሚ ስድብ ዘርጥጦት ሲያዋርደው አይተው ሁለቱንም ለ mutual self destruction ማበረታታት ነው።” ማየት አያስፈልገንም፡፡ አባዱላ ዛሬ አብዲ ፊጣን ባነካው በየቀኑ በታንክ የሚደፈጥጣቸውን የኦሮሞ ልጆች በስም እናውቃቸዋለን፡፡ ለነገሩ ጃዋር የሄደባት የ face saving መንገድ ማንም ብሔርተኛ በካምፑ ውስጥ ያለውን ቀውስ ለማረጋጋት የሚጠቀምበት የሰነበተ መሳሪያ ነው፡፡

የኦሮሞ ብሔርተኞች ስሌት እና የኦህዴድ ስሌት ግጭት

ጉዳዩን በጥልቀት ያሰበበት የኦሮሞ ልሂቅ ሁሉ እነደሚያውቀው በአሁነ ሰአት ኦሮሞን የመጨቆኛው ዋነኛ መሳሪያ ሌላ ሳይሆን ኦሮሞ ብሔርተኝነት እራሱ ነው፡፡ የኦሮሞ ብሔርተኝነት ዛሬ በአብዛኘው በሚሰበክበት እና በሚተገበርበት መልኩ እስከቀጠለ ድረስ በርካታ ብሔርተኞች እነደሚመኙት የኦሮሞ ሕዝብ ነጻ ማውጫ መሳሪያ ሳይሆን የኦሮሞ ሮሮ ዋነኛ ምንጭ እንደሆነ ይቀጥላል፡፡

እንዴት? ልክ ጃዋር እንዳስቀመጠው በአሁኑ ወቅት የኦሮሞ ብሔርተንነት ዋነኛ ትኩረት የኦሮሞ ልጆችን ከሌሎች Oromo vs the other ማሰባሰብ ማደራጀት ማነቃቃት ላይ ያተኩራል፡፡ ግቡም በአብዛኛው ለኦሮሞን እድል አስፈላጊ ከሆነ ኦሮሚያን እነደአዲስ አገር እሰከመገንባት ድረስ የራስን እድል በራስ የመወሰን መብትን በማስከበር ላይ ያተኩራል፡፡ ኦሮሞ ብሔርተኞች በዚህ ፕሮጀክት ሙሉ እምነት ኖሯቸው ከውስጥም ከውጭም ይሰራሉ እንበል፡፡ ይሄ አጀንዳቸው አጀንዳቸው ኦፒዲኦን እነደጠላት ሳይሆን እነደ ፕሮጀክቱ አንድ አካል አድርገው እንዲያዩ ይጋብዛቸዋል፡፡ ስሌታቸውም በአብዛኛው የሚቃኘው ዓለም እንዴት መስተካከል አለባት (Ought to be) በሚል ቅንኝት ነው፡፡ ምክንያቱም ትኩረታቸው አዲስ ስርዓት በመፍጠር የኦሮምን ጥያቄ በመመለስ ላይ ስለሚያደላ፡፡

ጋሼ ኦፒዲኦ ግን እነደ ኦሮሞ ብሔርተኞች ዓለም እንዴት መስተካከል እዳለበት ሲጨነቅ አይገኝም ፡፡ የጋሼ ኦፒዲኦ ዋነኛ ስሌት የተቃኘው ዓለም ዛሬ ላይ እንዴት ትንቀሳቀሳለች (What is the world like) በሚል ቅንኝት የተሰላ ነው፡፡

የኦህዴድ የሌት ተቀን ትልቅ ጭንቀት “ ዛሬ ላይ ባለው እውነታ ተመስርቼ ምን ያህል ሀብቴን አዳብራሉ ” ብቻ ነው፡፡ አባዱላ ወያኔ አለቆቹ ፊት ሲቀርብ “ለእኔ ፍርፋሪ ካልጨመራቹ ወየውላቹ ” ይላል፡፡ ሚኒሶታ ሲመጣ ደግሞ “ እኔኮ ባልሆን ኖሮ ትግሬው አገር ጨርሶ ነበር ” ብሎ እራሱን እነደ ተግባራዊ (Pragmatic) ታጋይ ያቀርባል፡፡

በዚህ ስሌት ስናየው አባዱለ እና ኦህዴድ በእጅጉን የሚጠቀሙት አሁን ያለው የኢትዮጵያ መዋቅራዊ እውነታ (Status Quo) ባለበት ሲቀጥል ብቻ ነው፡፡ በእነሱም መፍረድ ይከብዳል ከትቢያ ላይ አንስቶ ሚሊየን ዶላር ያስቆጠራቸውን ስርዐት ለምን ሲሉ ይገረስሳሉ ? ለኦህዴድ ከኦኤሜንም ጋር መቀመጥም ሆነ የኦሮሞ ብሔርተኞችን ማባበል በኦሮሞ ጥያቄ ላይ አንዳች ደንታ ስላለው አይደለም፡፡ በአለቆቹ ፊት የፍርፋሪ መጠን ማስጨመሪያ ምርጥ የመደራደሪያ ካርድ ግን ይሆኑለታል፡፡ ፍርፋሪ ስታንስ ጭምብል እየቀሩ ቢያስቸግሩት አይደል መለስ እያንዳንዱ ኦህዴድ ሲፋቅ ኦነግ ነው ያለው፡፡ ኦህዴድ እንዲህ በዳዴ እሄድ ቢበላ ክብር ይጎድለዋል እንጂ የስሌት ችሎታ ፈጽሞ አልጠፋውም፡፡

የሌንጮ ጉዞ ወደ ፊንፊኔ

ከስደት ወደውጪ አገርን እነደሚናፍቅ ፖለቲካዊ ያውም ኦሮሞ ፖለቲካዊ ሰው የሌንጮ ወደ አገርቤት መመለስ በብዙ መልኩ ያስደስተኛል፡፡ በመጀመሪያ የምደሰተው ለሌልጮ ለራሱ ነው፡፡ እስቲ የናፈቁት ዘመዶቹን አይን ይበት፤ እስቲ ላለፉት 20 ምናመን ዓመታት ያልደረሰቸውን ለቅሶዎች ይድረስበት፤ እስቲ ከልጅነት ጓደኞቹ ጋር ቁጭ ብሎ ይጫወትበት፤ እስቲ ከልጅነት መንደሩ ከሽማግሌዎቹ ጋር ቁጭ ብሎ ጠላ ይጠጣበት፡፡ ሌላዉ ሁሉ ይቅር ይህ ትልቅ ኦሮሞ ዋርካ ከብዙ ዘመን ስደት በኋላ እነደነ ሲሳይ ኢብሳ በአስከሬኑ ከተወለደበት አፈር ጋር ከሚገናኝ በሕይወት ሳለ በልጅነቱ ያቦካውን አፈር በሕይት ይየው፡፡ የሌንጮ መመለስ የመጀመሪያው ተግባር መንፈሳዊ እርቅ ለሌንጮ ማምጣት ነው፡፡ ይህ መንፈሳዊ ጥማት ፖለቲካዊ ሳይሆን ሞራላዊ ግብ ነው፡፡ ከአሊ ቢራ የባሰ የተሰደደ በስደትም ሳለ ስለሕዝቡ የጮኸ ማን አለ ግን በቃ ሳይሞት አፈሩን ማየተ ፈለገ ወደ አገርቤትም ገባ፡፡ የኦሮሞ አዙሪት እደው አሊቢራ ጮኽም ዝም አለም አላባራም፡፡

የእነ ሌንጮ መመለስ ግን ይሄነው የሚባል የፖለቲካ ለውጥ በኢትዮጵያ ላይ ያመጣል ብሎ መጠበቅ ተገቢ አይደለም፡፡ ሌንጮም ሆነ ፓርቲው ግፋ ቢል ኦህዴድ እና ወያኔ በሚያደርጉት የፍርፋሪ ድርድር ወቅት እርስ በእርስ የሚቀባበሉት የከረንቡላ ድንጋይ ከመሆን አይዘልም፡፡ የዘንድሮ ኦህዴድ ማለት ሌንጮ ትቶት የሄደው ኦህዴድ አይደለም፡፡ ዘንድሮ ኦህዴድ ሚሊየነር ደጋፊዎች እና አባላት ያሉት፤ የራሱ ትንንሽ ቡችሎች ያፈራ ትልቅ ውሻ ነው፡፡ ሌንጮ ኦህዴድን መቀላቀል እንኳ ቢያስብ በሩ ላይ ወረፋ ከያዙ በርካታ ግልገል ኦህዴዶች ጋር መፋለም ይኖርበታል፡፡ በፖለቲካው ተሳካለትም አልተሳካለትም ሌንጮ ለመንፈሱ ሲል ወደ አገሩ ይመለስ፡፡ ሌላውን አንኳን ዋቃ ይወስነዋል፡፡

The post ሌንጮ ለታ፤ ኦኤምኤን ፤ አባዱላ ገመዳ እና የሞራል ኪሳራ – እንደ ተጨማሪ ማብራሪያ appeared first on Zehabesha Amharic.

(ዜና ፎቶ) ታክሲዋ ባንክ ገባች

$
0
0

lada taxi
(ዘ-ሐበሻ) በኢትዮጵያ በተለይም ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የሚሰሙት የመኪና አደጋዎች እጅጉን እየበዙ መጥተዋል:: በየቀኑ የሚደርሰው የመኪና አደጋም በሰውና በንብረት ላይ እያደረሰ ያለው ጉዳት ተጽፎ የሚያልቅ አይደለም:: ከአዲስ አበባ ወሬዎች ያገኘነው የፎቶ መረጃ እንደሚያመለክተው ዛሬ የካቲት 4 ቀን 2007 ዓ.ም. ከእኩለ ቀን በኋላ መንገዷን ስታ በካዛንቺስ መናኸርያ መንገድ ከሚገኘው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ካዛንቺስ ቅርንጫፍ ጎራ ያለችው ላዳ ታክሲ በዚህ መልኩ ባንክ ገብታለች::

በንብረት ላይ የደረሰው አደጋ የታወቀ ሲሆን በሰዎች ላይ የደረሰው አደጋ በመጣራት ላይ ይገኛል::

The post (ዜና ፎቶ) ታክሲዋ ባንክ ገባች appeared first on Zehabesha Amharic.

(አሳዛኝ ዜና) ሲኖ ትራክ እና ሚኒባስ በመጋጨታቸው በተፈጠረ እሳት የ11 ሰዎች ሕይወት አለፈ

$
0
0

ዘ-ሐበሻ በተደጋጋሚ በኢትዮጵያ ውስጥ የሚከሰቱ አሳዛኝ የመኪና አደጋዎችን ስትዘግብ ቆይታለች:: ዛሬ ያገኘነው ዜና ደግሞ እሽጅግ አሰቃቂ ነው:: በቡራዩ ከተማ በደረሰ የመኪና አደጋና ተከትሎት በተነሳው የ እሳት ቃጠሎ የ11 ሰዎች ሕይወት ማለፉ ተዘገበ:: በቡራዩ ከተማ አስተዳደር ወረዳ ሁለት ልዩ ስሙ ቀርሳ በተባለ ስፈራ ትላንት ማምሻውን በደረሰ የትራፊክ አደጋ የ11 ሰው ህይወት ሲያልፍ ሁለት ሰው ላይ ከባድ ጉዳት ደርሷል ሲሉ መንግስታዊው ሚዲያዎች ዘግበዋል::
kataelo

እንደ ዘገባዎቹ ከሆነ አደጋው የደረሰው ትላንት ምሽት 1 ሰዓት ከ20 ደቂቃ ላይ ሲሆን፥ ወደ አዲስ አበባ ይመጣ የነበረ ሲኖ ትራክ የጭነት ተሽከርካሪ ከሚኒባስ ጋር በመጋጨቱ ነው አደጋው የደረሰው። በዚህ አደጋ የተነሳም የ11ዱ ሰዎች ሕይወት ማለፍ ምክንያት ሲሆን ሲኖ ትራኩ ላይ የነበሩት ሹፌር እና ረዳት ከአደጋው መትረፍ ቢችሉም በሚኒባሱ ውስጥ የነበሩ ከ11 የሚበልጡ ሰዎች በተነሳው እሳት ተቃጥለው ህይወታቸው ማለፉን ፖሊስ ለመንግስት ሚዲያዎች አስታውቋል::

The post (አሳዛኝ ዜና) ሲኖ ትራክ እና ሚኒባስ በመጋጨታቸው በተፈጠረ እሳት የ11 ሰዎች ሕይወት አለፈ appeared first on Zehabesha Amharic.

  የተስፋ ጣዝማ –የአሻም ብራ! -ሥርጉተ ሥላሴ

$
0
0

ከሥርጉተ ሥላሴ 17.02.2015 /ዙሪክ – ሲዊዘርላንድ/

Haile Medhin Aberaዛሬ የካቲት 17 ቀን 2015 ጀግና ሃይለመድህን አበራ የአሻምን ብራ ችቦ ጄኔባ ላይ በተግባር ያዘመረበት ዕለት ነው። ልክ አመቱ። አሻም የወያኔ ሃርነት ትግራይ ማንፌስቶ በማለት በዝምታ፤ አንዲት ቆራጣ ንብረት ሳይወድም፤ አንድ ትንፋሽ ከመኖር ሳይቋረጥ፤ በእንግዶቹ ላይ ምንም ዓይነት የመንፈስ ጫና ሳይፈጥር የወጣትነቱን ፍላጎት ሁሉ ፈቅዶና ሰውቶ ጸጥ በላ ጭምታዊ መንገድ ገዢ መሬቱን የተቆጣጠረበት ዕለት ነው። ዕለቱ የወገኖቻችን ሆነ የሌላ ሀገር ዜጎችም ነፍስ ሳይጠፋ ወይንም ሳይቀጠፍ፤ ጥቁር ሳይለበስ ወይንም ደም ሳያበቅልበት ትሁት በሆነ የሰብዕዊነት ሥነ – ምግባር ጎርብጦኛል ያለውን የወያኔ አስተዳደር የታገለበት፤ ደግሞም የረታበት የሰላማዊ ትግል ውጤት ነጥሮና ጎልቶ የወጣበት ልዩ ዕለት። ተባረክ የእኔ ጌታ! አሳዳጊህንም ይባርካው አምላኬ። አሜን!

ከእሱ ሰላማዊ ውጤት በኋላ እስያ ላይ ሰፊ የሆኑ ተደጋጋሚ የአውሮፕላን አዳጋዎች ደርሰዋል። የፍጥረት እልቂቶች፤ የንብረት ጥፋቶች፤ የሀብት ብክነቶች በተከታታይ ታይተዋል። በዛች ቀውጢ ሰዓት ሰማይ ላይ የፍጥረት መንፈስ ውጥረት የቤተሰብና ዬአለም ማህበረሰብ ጭንቀትና ጥበት ሲታሰብ ደግሞ መስፈርያ የለውም። በፍጹም። አስተዋዩ የተስፋ ጣዝማ ግን ፍውስት ነበር ማለት ይችላል። ሊገመቱ የማይችሉ የመንፈስ ጫናዎችን ሁሉ ነበር በብልሃት አስቀድሞ – የታደገው። ሂደቱም ውጤቱም ልባም ነበር። ቀንበጡ በሰከነ፣ በበሰለ፤ በተባ፤ በቀላማም ንድፍ ተክህኖ ለድል በቃ። ድሉ የዓለም ማህበረሰብ ሁሉ ነው። የሰው ልጅ ህይወትን እንዲህ ባስተዋለ መንገድ ማዳን በኽረ ውጤት ነውና። ስለሆነም ጀግናዬ ሃይለመድህን አበራ በማስተዋል ዕለቱን – ዘርቶ – አብቅሎ አፍርቶና – ፈርቶም አሳዬ። ኑርልኝ የእኔ አባት!

እንሆ ጊዜ ታሪክን ይሰራል። ፍቅርን የተረጎሙት ዶር. ሼክስፔር ፈይሳም ከሀገረ አሜሪካ ወደ ሲዊዝ ጄኔባ ተጉዞው የአካላቸውን ሁኔታ ለማዬት ፍቅርን ለፍቅር ጃኖ አለበሱ። ፍቅር ስለ ቃሉ ፍቅር መሆኑ ብቻ ሳይሆን ፍቅር ሲሆኑት ተግባሩ እራሱ ፈክቶ ይተረጉማል። ለዜግነታቸው፤ ለብሄራዊ ክብራቸው፤ ለወገኖቻቸው ችግር ቅርብ በመሆን፤ ለንጹህ ወንድማዊ መንፈሳቸው እራሳቸውን ማግደው በመከራ ቀን አብረው በመገኘት ታሪክን እንሆ ጻፉ። ሙያና ሥነ – ምግባርም ፍሬ አፈሩ! ትውልዱን አፈለቁት – በፍቅር። ትውልዱን አስመሰገኑት – በተስፋ። ትውልዱን አስባረኩት – በደግነት፤ ትውልዱን አበረታቱት – ሆነው በመገኘት። ከተሟላ አክብሮት ጋር ምስጋና ብቻ ሳይሆን የእርሳቸውም ተማሪ መሆኔን በአጋጣሚው ልገልጽ ወደድኩኝ። ሰው እንዲህ ሲኖር ጨለማው – ይነጋል። የተቀደደው ተስፋ – ይጠገናል። የዛለው ክንድ ብርታትና ኃይል ያገኛል። አብነት – የዘመናት። ድንግል ትጠብቅልን! አሜን! የዘመን – ዋርካ።

ከዚህ በተረፈ በምልዕት የወንድማቸውን ችግር የተጋሩ፤ ፊት ለፊት ወጥተው የመሰከሩ፤ ምስክርነቱን ያዘከሩ፤ ለዝክራኑ ፈቃድ በመስጠት ያተሙ – ያሰራጩ፤ በብርድ በቁር የተንገላቱ ድምጻቸውን ከፍ አድርገው ጀግናችን ያሉ፤ ስለ እሱ የተቆረቆሩ – የተንገበገቡ ሁሉ ዋጋ ከፋዩ አምላክ ነውና እኔ እንደ አንድ ሀገር ወዳድ ዜጋ አምላክ በያሉበት በስውር ዋጋቸውን ይክፈል እላለሁ። እግዚአብሄር ለወግ አብቅቶትም ውለታቸውን በአንደበቱ ለመመስከር ያብቃው። አሜን!

ማህጸነ ሲዊዝም ደግ ናትና እፍን ሽክፍ አድርጋ፤ ሽሽግ አድርጋ ስለያዘችው፤ በዕንባው ቀን በመገኘት ዕንባውን ስላበሰችም የከበረ ምስጋና ለኮሽ አይሏ ሲዊዝም ይደረስ ብያለሁ። በተረፈ መንገዱ እርጥብ ነበር። ጉዞው የተሳካ ነበር። ይሄው ልክ በዓመቱ መግቢያ መባቻ የአውሮፓ አህጉራዊ ድርጅት ከአንድ ግልጽ፣ ወሳኝ አቋምና ውሳኔ ደረሰ። ከእንግዲህ በኋላ አውሮፓ ላይ ያለ የወያኔ ሃርነት ትግራይ ማንፌስቶ አስፈጻሚ ደጋፊ፤ ተባባሪ፤ ኢንባሲ፤ ቆንሲላ ጽ/ቤት፤ የስለላ ድርጅት ምን ሥራ ሊኖራቸው እንደሚችል አምላክ ይወቀው። የቅጥፈቱ የሎቪ ሥራው በር ተከርችሟ ሥራ ፈላጊ አድርጓቸዋልና። ከእንግዲህ ጆሮ የለውም አውሮፓ ….. ለወያኔ ሃርነት የተዛባ መረጃ። እኛም እልልልል – አልን –

ይህ በራሱ የካፒቴን ሃይለመድህን ውሳኔ ትክክለኛነት ዕውቅና ያሰጠዋል። ቢከፋው ነው። ባይመቸው ነው ከሚል ዕድምታ ያደርሳቸዋል። ስለዚህ ለዘለቄታ ኑሮው፤ ተስፋው፤ ህልሙ ሰፊ የሆነ የሰላም መስመር ይመሰልኛል። ጥግ አልቦሽነት በስደት፣ ከስደቱ በላይ የከፋው ገጠመኝ ነው። ስደት በራሱ ጨለማ ነው። አድማጭ ሲጣፋ ደግሞ ቀኑም ጨለማ ይሆናል። የጨለማ ጉዞ ደግሞ መሰናክሉን አልፎ ለመሄድ ጋዳ* ነው። አሁን ግን አነሰም በዛም ብርሃን አለ …. ብርሃኑ ቀርቦ ለሁሉ ይዳረስ ዘንድ ደግሞ  ከፈጣሪ ጋር የሁሉም ተሳትፎ በቅንነት ከታከለበት ንጹህ ልቦና የማሸነፍ አቅም ነውና – ነገ ይነጋል።

በተረፈ ዕለቱን በማሰብ እንደምትችሉት ብታደርጉ ደስታዬ ነው። ግን ትእዛዝ አይደለም ትሁታዊ አስተያዬት እንጂ። ውጤትን ማክበር፤ መስዋዕትነትን መጠበቅ የአደራ ድሪ ይመስለኛል። ተከታይንም ያነሳሳል – ያበረታታል። በተረፈ ዘሃበሻን ከልብ አመሰግናለሁ። በዬወሩ የምልካቸውን ጹሑፍ ካለመሰልቸት ነበር የሚያወጡልኝ። ያቆምኩትም እራሴ ነኝ። የአላጋጩን የወያኔን ምርጫ በሚመለከት በርካታ ጸሐፍት ሃሳባቸውን እዬገለጹ ስለሆነ ቦታ ላለመሻማት በሚል። ነገር ግን በወር ሁለት ጊዜም በተስፋ ማህጸን ጀግናዬ አበራ ሀይለመድህን በቋሚነት ተግባሩ ይነግሣል – በጸጋዬ ራዲዮ። መሸቢያ ሰሞናት – ውዶቼ!

መፍቻ ….. ጣዝማ* … የማር ዓይነት ነው። የሚገኘው ግን ቆላ ገደል ውስጥ ነው። በሌላ በኩል ጣዝማ የቀለም ዓይነትም ነው። ጣዝም ቀለሙ በቅቅል ዶሮቄት የሚዘጋጀው በጎጃምና በጎንደር የጠላ አጠማመቅ ሂደት እስከ መንፈቅ ዓመት ሲቆይ መልኩ ጣዝም ዓይነት ይሆናል። ወይንም የድፍድፉ ሊፍተር ቀለሙ ጣዝማ ቀለም ነው። ጣዝማ ማር አይነጠረም። እራሱ ሲፈጠር የተነጠረ ነው። ሌላው የማር ዓይነት ግን በፀሐይ ይነጠራል። ስለዚህ ጣዝማ ጣጣውን የጨረሰ ኮለል ያለ የጠራ መሆኑ ብቻ ሳይሆን ጣዝም ቁጥር ሊወጣላቸው የማይችሉ በሽታዎች ፈዋሽ መዳህኒት ነው። በቀላሉም ገብያ ላይ አይገኝም። ውድም ነው። ጣዕሙም ሆነ ይዘቱ የተለዬ ነው። ስለዚህ ካፒቴን ሃይለመድህን አበራ ለእኔ የተስፋ ጣዝማዬ ነው።

*ሊፍተር – ከጥሩ ጠላ ይለያል። ድፍድፉ በወፍራሙ ይዘለልና በከረጢት ይታሰራል። ከዛ ጭማቂው ሊፍተር ይባላል። በጣም ሃይለኛ ነው። የኢትዮጵያ ውስኪ ልበለውን ከቶ …. እንደዛ። ግን ሊፍተር የረጅም ጊዜ ድፍድፍ ብቻም ላይሆን ይችላል በአፍለኛ ድፍድፍም ይዘጋጃል። ከነጭ ጠላም* ሊፍተር ይዘጋጃል።

*ነጭ ጠላ —- ብዙ ጊዜ ነጭ ጠላ በዳጉሳ ነው የሚዘጋጀው። ነጭ እንዲሆን ሲፈለግ አብሽሎው አነባበሮ ዓይነት ይሆንና በብረት ምጣድ ሳይሆን በሙጎጎ /በምጣድ/ ነው የሚጋገረው። ከላይ እንደጠቀስኩት ከነጭ ጠላ ድፍድፍም ሊፍተር ማዘጋጀት ይቻላል። ግን እንደ ተለምዷዊ ድፍድፍ ጠላውና እንደ ዕድሜ ጠገቡ የቅቅል ዶሮቄት ድፍድፍ የብርቱነት አቅሙ እንደ አቅሙ ይሆናል።

ጋዳ* ከባድ ችግር፣ መፍትሄው ሩቅ ወይንም ቀላል ያልሆነ እንደ ማለት ነው፤

ብራ* ጭፍግግ ያለው ጨቅጫቃ አረንቋ ቀን ተሸኝቶ ወለል ባለው ሰማይ ላይ ብርሃን ሲነግሥ ….. ሰውነትም ቅልል ብሎ ለማናቸውም ግዳጅ በብቃት ሲዘጋጅ …. ወዘተ …..

ጀግኖቻችን መርሆቻችን ናቸው!

እግዚአብሄር ይስጥልኝ!

 

 

The post   የተስፋ ጣዝማ – የአሻም ብራ! -ሥርጉተ ሥላሴ appeared first on Zehabesha Amharic.

Viewing all 15006 articles
Browse latest View live