Quantcast
Channel: Ethiopian News | ዘ-ሐበሻ | Latest News Provider | News For All
Viewing all 15006 articles
Browse latest View live

ወያኔ ኢትዮጵያን አፍርሶ ወደ ጉሬው ለመግባት

0
0

ሞረሽ ወገኔ የዐማራ ድርጅት     ቅዳሜ ጥር ፪ ቀን ፪ሺህ፯  ዓ.ም.                         ቅፅ ፫ ፣ ቁጥር ፰

የመጨረሻ መሠናዶውን እያደረገ ነው
· የትግሬ-ወያኔዎች ከተለያዩ ጎሣዎች እና ነገዶች ሰዎችን መልምለው እና አደራጅተው፣ እንዲሁም የወታደራዊ፣ የደህንነት፣ የአደረጃጀት፣ የአመራር እና የቁጥጥር ሥራ የሚሠሩ የትግሬ-ወያኔዎች መድበው በከፍተኛ ሚሥጢር ኢትዮጵያን የማፈራረስ ሤራ እየተዶለቱ መሆኑን በተጨባጭ መረጃዎች አረጋግጠናል።

moreshየትግሬ-ወያኔ የመጨረሻ ግብ ኢትዮጵያን በመበታተን፣ የትግራይ ረፑብሊክ መመሥረት መሆኑን በ1968 ዓ.ም. ይፋ ባደረገው ፕሮግራሙ መሠረት ላለፉት ፵(አርባ) ዓመታት ያደረገው ጉዞ ያሣያል። በጉዞው የኢትዮጵያን የረጅም ዘመን ታሪክ ክዶ በመቶ ዓመት መገደቡን፣ የትግሬ-ወያኔ መሪዎች እና አባሎች በተደጋጋሚ በጻፉዋቸው መጻሕፍት እና በየአጋጣሚው ባደረጉዋቸው ንግግሮች ለሕዝብ ይፋ ማድረጋቸው ይታወቃል። «ኤርትራ በኢትዮጵያ በቅኝ ግዛትነት የተያዘች ናት፤ ስለሆነም ሻዕቢያ የሚያካሂደው የመገንጠል እና የነፃነት ጥያቄ ተገቢ እና ትክክል ነው።» ብለው፣ ከሻዕቢያ በላይ ሻቢያ ሆነው፣ የትግራይን ልጆች የጦር ማገዶ በማድረግ ኤርትራን ማስገንጠላቸው ማንም ሊያስተባብለው የማይችለው ሃቅ ነው። ኢትዮጵያውያንን እንደ አንድ ሕዝብ ያስተሳሰሩ የወል ዕሴቶችን፥ «የኢትዮጵያዊነት አገራዊ እና ብሔራዊ ስሜት የሁሉም በኢትዮጵያ የሚኖሩ ነገዶች እና ጎሣዎች ሳይሆኑ፣ የዐማራው ብቻ የማንነት መገለጫዎች ናቸው፤ ዐማራው ጨቋኝ እና በዝባዥ ነገድ ነው፤ እርሱን ሁሉም ነገዶች እና ጎሣዎች በወያኔ መሪነት ተባብረው ማጥፋት አለባቸው።» በማለት በከፈቱት የዘር ማጥፋት እና የዘር ማጽዳት ጦርነት፣ የኢትዮጵያዊነት የወል ዕሴቶችን፣ ተቋሞችን፣ ግንኙነቶችን፣ አሠራሮችን ወዘተርፈ በማጥፋታቸው ዛሬ አገሪቱ እና ሕዝቧ የሚገኙበት ሁኔታ በግልጽ ያሣያል። የአገሪቱ ዘመን-ጠገብ መልከዐ-ምድራዊ መለያ ስሞች እና ወሰኖች ተሽረው በተወሰኑ ነገዶች ማንነት ብቻ ላይ የተመሠረቱ ስሞች በመስጠት፣ የኢትዮጵያውያንን ተዘዋውሮ በፈለጉት ቦታ እና አካባቢ የመኖር እና የመሥራት ተፈጥሮአዊ፣ ታሪካዊ፣ ባህላዊ እና ሰብአዊ መብቶቻቸውን ገፍፈው፣ አንድነታቸውን አሣጥተው፣ አብሮነታቸውን ክደው፣ በጠላትነት እንዲተያዩ አድርገዋቸዋል። ኢትዮጵያ እና ኢትዮጵያዊነት ከሕዝቡ ስሜት ፈጽሞ እንዲጠፉ መጠነ ሠፊ የሆነ የሥነልቦና ጦርነት ከፍተው አገሪቱን ከመጨረሻው የጥፋት ጠርዝ ላይ አድርሰዋት ይገኛሉ።

የትግሬ-ወያኔ እና ተከታዮቹ በኢትዮጵያ ግዛታዊ አንድነት፣ ሉዓላዊነት እና ብሔራዊ ጥቅም፣ እንዲሁም በሕዝቧ ኢትዮጵያዊ ማንነት ላይ ታሪክ፣ ትውልድ፣ ሕግ እና ማናቸውም ዓይነት ሥነ-ምግባር ይቅር ሊለው የማይችል የክህደት ተግባሮችን የፈጸሙ መሆኑን ከማንም ይበልጥ ራሣቸውም አይክዱም። ይህም በመሆኑ የኢትዮጵያ አንድነት ተጠብቆ ከዘለቀ በየትኛውም ጊዜ በአገር ክህደት ወንጀል ተጠያቂ እንደሚሆኑ ያውቃሉ። ከዚህ ተጠያቂነት ለመዳን እንችላለን ብለው የሚምኑት ሁለት ነገሮችን ጎን ለጎን ማከናወን ሲችሉ ብቻ ነው። እነዚህም፦ አንደኛ የወያኔ ትውልድ ለሚቀጥሉት መቶ ዓመታት በኢትዮጵያ ፖለቲካዊ እና ኢኮኖሚያዊ ሕይዎት ላይ የወሳኝነቱን ሚና ይዞ የሚቀጥልበት አስተማማኝ ሁኔታ ሲረጋገጥ፤ ይህ የመጀመሪያው ዕቅድ በተለያዩ ምክንያቶች ባይሣካ ሁለተኛው አማራጭ ዕቅድ ትግራይን ከኢትዮጵያ በመገንጠል የትግራይ ረፑብሊክ በመመሥረት ጎጆ መውጣት፤ የሚሉ ናቸው።

ሁለተኛውን ግብ ለማሣካት በኢትዮጵያ ላይ ሥልጣን ከተቆጣጠሩ ጊዜ ጀምሮ ለምትገነጠለው ትግራይ ቁሣዊ፣ ቴክኒካዊ እና ኅሊናዊ ሁኔታዎች እንዲሟሉ የሚያስችሉ ተግባሮችን ማከናወን እንዳለባቸው ታሣቢ አድርገው መንቀሣቀሣቸው ባለፉት ፳፫(ሃያ ሦሥት) ዓመታት የሥልጣን ዘመናቸው ትግራይ ውስጥ አያሌ የመሠረተ ልማት ሥራዎች መሥራታቸው ይታወቃል። በዚህም መሠረት የትግራይ ክልል ከጎንደር እና ከወሎ ክፍለ ሀገሮች መሬት ነጥቀው በታሪክ የትግራይ አካል ሆነው የማያውቁ አካባቢዎችን አጠቃልለው ጥንተ-ነዋሪውን የዐማራ ነገድ አባላት የሚገድሉትን በመግደል፣ ቀሪውን በማሠር እና በማሰደድ ትግሬን አስፍረውበታል። ይህ የያዙት ግዛት ወደፊት ለምትገነጠለው ትግራይ ይጠብባል በማለት ከሰቲት ወደ ደቡብ ምዕራባዊ የጎንደር እና የጎጃምን የሱዳን አዋሳኝ ወረዳዎችን ከቤንሻጉል ጉምዝ እና ጋምቤላ ክልሎች ጋር በማገናኘት የታላቋ ትግራይን የመሥፋፋት ዓላማ ዕውን በማድረግ ላይ ይገኛሉ (አባሪ ካርታውን ይመልከቱ)።

በዚህም መሠረት ለወደፊቷ ትግራይ ለምትጠቀልለው ሠፊ ግዛት፣ ከውጭው ዓለም ጋር የሚያገናኙ የመገናኛ መሥመሮችን ዘርግተዋል፣ ተጨማሪ መሥመሮችንም በፍጥነትም በመገንባት ላይ ይገኛሉ። የትግራይን ምርት ወደ ውጭ ለመላክ እና ከውጭ የሚፈለጉ ሸቀጦችን ወደ ውስጥ ለማስገባት፣ ከጅቡቲ እስከ መቀሌ፣ ከሱዳን ጠረፍ እስከ መቀሌ የሚያገኛኙ የባቡር ሐዲድ ግንባታዎች በመፋጠን ላይ ናቸው። ሁለት ታላላቅ ዓለም አቀፍ የአውሮፕላን ጣቢያዎች መቀሌ እና አክሱም ላይ ገንብተዋል። ቀበሌዎችን ከወረዳ ከተሞች፣ ወረዳዎችን ከአውራጃዎች (ዞኖች)፣ አውራጃዎችን ከዋና ከተማዋ ከመቀሌ ጋር የሚያገናኙ፣ ክረምት ከበጋ ያለምንም እንከን አገልግሎት የሚሠጡ መረብ-መሰል አውራ መንገዶች ተገንብተዋል። ድርቅን ለመቋቋም የክረምት ዝናብን ለማቆር የሚያስችሉ በርካታ ግድቦችን ሠርተው አገልግሎት ላይ አውለዋል። የትግራይን አዲሱን ትውልድ ከኢትዮጵያዊነት ስሜት አውጥቶ የትግራዊነት ስሜት እንዲገነባ የሚያስችሉ፣ በተቀነባበረ ሁኔታ ቅስቀሣ እና ትምህርት በማያቋርጥ መልኩ የሚሰጡ ተቋሞች ተገንብተዋል። በርካታ ትምህርት ቤቶች፣ ኮሌጆች፣ የቴክኒክ እና የሙያ ትምህርት ቤቶች፣ ዩኒቨርስቲዎች ተከፍተዋል። በኢንዱስትሪ ግንባታ ረገድ የነባሮቹን የኢትዮጵያ ፋብሪካዎች ሕልውና የሚያጠፉ የመድኃኒት፣ የጨርቃጨርቅ፣ የስሚንቶ፣ የመጠጥ እና የብረታ ብረት ፋብሪካዎች በሁሉም የትግራይ አውራጃዎች ተቋቁመዋል። ከእነዚህ መካከል፦ የአዲግራት መድኃኒት ፋብሪካ፣ እንዲሁም መቀሌ የተገነቡት የመሰቦ ስሚንቶ ፋብሪካ፣ የአልሜዳ የጨርቃጨር ፋብሪካ፤ የመሥፍን ኢንጂነሪንግ የብረታ ብረት ኢንዱስትሪ፣ ወዘተርፈ ለአብነት የሚጠቀሱ ናቸው። አሽጎዳ አካባቢ በአፍሪቃ በግዙፍነቱ ቀዳሚ የሆነ እና በነፋስ ኃይል ኤሌክትሪክ የሚያመነጩ ተርባይኖች በብዛት ተገንብተዋል።

የአገሪቱ የፖለቲካ እና የኢኮኖሚ መዋቅሮች ያላአንዳች ይሉኝታ በወያኔች የተያዙ ናቸው። የአገሪቱን የአየር እና የምድር ኃይል መከላከያ የማዘዣ ማዕከሎች ከአዲስ አበባ እና ከደብረዘይት በማስወጣት ማዕከላዊ ዕዛቸውን ትግራይ ላይ እንዲሆን በማድረግ ወሣኝ የሆኑት የመከላከያ መሣሪያዎች ትግራይ ውስጥ እንዲከማቹ ተደርጓል። የከባድ ሮኬቶች መተኮሻ መንኮራኩሮች ትግራይ ውስጥ ተገንብተዋል። የአገሪቱ የመከላከያ ኃይል ከጓድ እስከ ጠቅላይ ኤታማጆር ሹም ድረስ ያሉት ቁልፍ የአዛዥነት፣ የመገናኛ፣ የድርጅት፣ የሎጂስቲክ ኃላፊነቶችን በሙሉ በትግሬዎች በማስያዝ የወታደራዊ ተቋሙ ሁለንተናዊ እንቅስቃሴው የትግራይን መገንጠል ዕውን በሚያደርግ መልኩ ወደፊት እየተባለ ይገኛል።

በአጠቃላይ የትግራይን ግንጠላ ዕውን መሆን ሂደቱ የተመቻቸ እንዲሆን፣ በ«ሽግግር ዘመን» ተብየው «ልማት ቅድሚያ በጦርነት ለተጎዱ ክልሎች» በሚል ስም የአገሪቱ አጠቃላይ በጀት ለትግራይ ልማት ተመድቦ ለአምስት ዓመታት ከላይ ለተጠቀሱት ተግባሮች እንዲውል መደረጉ ይታወቃል። ከሽግግር መንግሥቱ ፍጻሜ በኋላም የተዘጋጀው «ሕገመንግሥት» ተብየው የሽግግር መንግሥቱ ቻርተር ተከታይ ሆኖ በመዘጋጀቱ፣ አጠቃላይ ያለፉት ፳፫(ሃያ ሦሥት) ዓመታት ሲሠራ የኖረው ከፍ ሲል የተጠቀሱትን ሁለት ግቦች ለማሟላት፣ ማለትም፦ የትግሬ-ወያኔ ትውልድ ለመቶ ዓመታት በኢትዮጵያ ሥልጣን ላይ የሚቆይበትን ሁኔታ እያረጋገጡ መጓዝ፣ ይህ የማይሆን ከሆነ ለምትገነጠለው ትግራይ ቁሣዊ፣ ቴክኒካዊ እና ኅሊናዊ መሠረት ሊሆኑ የሚችሉ የሁለንተናዊ ግንባታ ተግባሮችን በተጓዳኝ ማከናወን የሚለው በተደጋጋፊ መልኩ ሲሠራ መቆየቱ ይታወቃል።

ይህ ሁሉ ሤራ ቢጎነጎንም፣ የትግሬ-ወያኔ ባልጠበቀው መልኩ የኢትዮጵያዊነት ስሜት ከሕዝቡ ኅሊና ውስጥ ከመፋቅ እና ከመደብዘዝ በተቃራኒ፣ የበለጠ እየጠነከረ መሄዱ የአደባባይ ምሥጢር ነው። ለዚህ ማረጋገጫዎች በተከታታይ በሚነሱ ሕዝባዊ ተቃውሞዎች እና በተቃዋሚ ኃይሎች መበራከት ናቸው። ስለዚህ የትግሬ-ወያኔ ቡድን «ለመቶ ዓመታት በኢትዮጵያ የፖለቲካ ሥልጣን ላይ እቆያለሁ» የሚለው ዓላማው ሊሣካ የማይችል እንደሆነ፣ ከሁሉም በላይ ደግሞ በ፲፱፻፺፯ (1997) ዓ.ም. ብሔራዊ ምርጫ በማረጋገጡ፣ አጠቃላይ እንቅስቃሴውን «ትግራይን ከቀሪዋ ኢትዮጵያ መገንጠል» በሚለው ሁለተኛ ግቡ ላይ እንዲያተኩር ሁኔታዎች እንዳስገደዱት ይታያል። ለዚህ የግንጠላ ዓላማው ያጸደቀው «ሕገመንግሥት» ተብየው ዋናው መሣሪያው መሆኑ ይታወቃል። አንቀፅ ፴፱(ሰላሣ ዘጠኝ) ለማንም ጥቅም ተብሎ ሣይሆን፣ የትግራይን ግንጠላ ለማሣሳካት የተቀረጸ አንቀፅ እንደሆነ ማንም ይስተዋል አይባልም። ዛሬም ቢሆን የትግሬ-ወያኔ የተመሠረተበትን ዋናውን ስሙን (ሕዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ) ያለመቀየሩ የሚያረጋግጠው ሃቅ ትግራይን ከቀሪዋ ኢትዮጵያ መገነጠል በይደር የቆየ የማይቀር አጀንዳው መሆኑን ነው። ይህ ዕውነት እንደተጠበቀ ሆኖ በዚህ አንቀፅ ብቻ ትግራይን ገንጥሎ በሰላም መኖር እንደማይችል የትግሬ-ወያኔ ጠንቅቆ ያውቃል። የትግሬ-ወያኔ መሪዎች ከተጠያቂነት መዳን የሚችሉት፣ ከኢትዮጵያ ሕዝብ የዘረፉትን ንብረት መጠቀም የሚችሉት፣ የትግራይ መገንጠል ለጊዜውም ቢሆን ዕውን ሊሆን የሚመችለው፣ በቀሪዋ ኢትዮጵያ ነገዶች መካከል መበታተን ሲፈጠር፣ ከሁሉም በላይ ዐማራ የተሰኘውን ነገድ ሌሎች ነገዶች በጠላትነት ፈርጀው እርሱን ማዳከም ሲችሉ፣ እንዲሁም «ዐማራ» ሲል የከለለውን ክልል ከውጭ አገር ጋር እንዳይገናኝ ዝግ በማድረግ ብቻውን አቁሞ ኅልውናውን ማጥፋት ሲቻል እንደሆነ ብቻ መሆኑን ይህ ቡድን አቅዶ በተግባር ሲንቀሣቀስ ቆይቷል። ለዚህም ባለፉት ዓመታት ሁሉም በሚባልበት ደረጃ በአገሪቱ ውስጥ የሚገኙት ነገዶች ዐማራውን በአውራ ጠላትነት ፈርጀው የጥፋት እጃቸውን እንዲያነሱበት አድርጓል።

የትግሬ-ወያኔ ምዕራባዊውን «የዐማራውን ክልል» ለም እና ድንግል መሬቶች ለሱዳን በገጸበረከት ሰጥቷል። በቀረው ምዕራባዊ ዳርቻ የትግራይን ግዛት በማስፋት ከቦ፣ ከቤንሻጉል ጉምዝ እና ከጋምቤላ ክልሎች ጋር አገናኝቷል (አባሪ ካርታውን ይመልከቱ)። ከ5 ሚሊዮን የማያንስ ዐማራ ከምድረ ኢትዮጵያ አጥፍቷል። አያሌ ዐማሮች በአገር ውስጥ ሠርቶ የመኖር መብታቸውን በመገፈፋቸው ለስደት ሕይዎት ተዳርገዋል። በስደት በዓለም ዙሪያ ከሚኖረው ኢትዮጵያዊ መካከል ከመቶ ፷(ስድሣ) እጁ በላይ ዐማራ መሆኑ የሚያመለክተው፣ ዐማራው በገዛ አገሩ ሠርቶ የመኖር መብቱን የተገፈፈ መሆኑን ብቻ ሣይሆን፣ ዐማራው በመጥፋት ሂደት ላይ መሆኑን የሚያሣይ ነው።

ሰሞኑን ለሞረሽ ወገኔ ዐማራ ድርጅት ከደረሱት እጅግ አስተማማኝ መረጃዎች መካከል፣ ወያኔ በኢትዮጵያ ፖለቲካ አናት ላይ የመቆየት ዓላማው የማይሣካ መሆኑን ተገንዝቦ፣ ወደ ሁለተኛው እና የመጨረሻ ግቡ፣ ማለትም፦ ትግራይን ለመገንጠል በከፍተኛ ሚስጢር እየሠራ መሆኑን የሚያረጋግጡ ናቸው። ይህም የትግራይ ግንጠላ ዕቅድ ለማሣካት እንዲቻል፣ ከአገር ውስጥ ተቃዋሚ ኃይል እንዳይነሣ፣ ኢትዮጵያን በሽግግር ዘመኑ ከፋፍለዋት በነበረው ፲፬(አሥራ አራት) እና ከዚያም በላይ የሆኑ የክልል ወሰኖችን የሚያመለክቱ ካርታዎችን አዘጋጅተው፣ ከየጎሣው ሰዎችን መልምለውና አደራጅተው፣ ለነዚህ ሰዎች የወታደራዊ፣ የደህንነት፣ የአደረጃጀት፣ የአመራር እና የቁጥጥር ሥራ የሚሠሩ የትግሬ-ወያኔዎች ተመድበው በከፍተኛ ሚሥጢር ፀረ-ኢትዮጵያ ሤራ እየተዶለተ መሆኑን አረጋግጠናል። ይህም ከ1997 የምርጫ ሽንፈታቸው ማግሥት ጀምሮ በመከናወን ላይ ያለ ተግባር እንደሆነ የመረጃ ምንጮቻን ገልፀውልናል። «ይህ አይሆንም፣ አይደረግም፣ አይታሰብም» ሊባል የማይችል እንደሆነ የወያኔ ጉዞ እና ተግባር ከጥርጣሬ ውጭ በሆነ መንገድ ያስረዳናል። ለዚህ ሤራቸው ማረጋገጫዎቹ በነባር ኢትዮጵያዊ እምነቶች መካከል እየሰራ ያለው የማጥፋት ሥራ፤ በጎጃም፣ በጎንደር፣ በአዲስ አበባ፣ በሶማሌ፣ እየተካሄዱ ያሉት የጥፋት እርምጃዎች የዚህ ዕቅድ አካሎች መሆናቸውን ልብ ሊባል ይገባዋል።

ሌላው የትግሬ-ወያኔ ኢትዮጵያን የማፈራረስ ተልዕኮው የማይቀር እና የፍጻሜው የመጨረሻ ደረጃ ላይ መድረሱን ማሣያው፣ የምዕራቡ ዓለም የመረጃ እና የስትራቴጂክ ጥናቶች ተቋም ባለፈው የአውሮፓውያን ዓመት አጋማሽ ላይ በ2030 እ.አ.አ. ከዓለም ካርታ ላይ ከሚጠፉ አገሮች አንዷ ኢትዮጵያ መሆኗን ይፋ ማድረጉን እናስታውሳለን። በተመሣሣይ ሁኔታ በኅዳር ወር ፪ሺህ፯ ዓ.ም. ሞስኮ ውስጥ የተካሄደ የዓለም አቀፍ ቀውሶች ጥናት ተቋም ባዘጋጀው ስብሰባ፣ በምሥራቅ አፍሪካ የሚታየውን ብጥብጥ ለዘለቄታው ለማስወገድ የምሥራቅ አፍሪካ አገሮች ኮንፌደሬሽን መመሥረት እንዳለበት ግፊት የሚያደርግ ጥናት ቀርቧል። የኮንፈደሬስሽኑ አባል አገሮች ጥንት እንግሊዝ «ከኢትትዮጵያ ተቆርሶ ወደ ሱዳን ይካተት» ትለው የነበረው የኤርትራ ምዕራባዊ ክፍል ወደ ሱዳን ተካልሎ ሱዳን ከሦስት እንድትከፈል፣ የኤርትራ ደጋማው ክፍል ከትግራይ ጋር ተቀላቅሎ ትግራይ ትግርኝ የተሰኘ ግዛት እንዲፈጠር፣ የአፋርኛ ተናጋሪዎች በአንድ ግዛት ተጠቃለው አንድ ግዛት እንዲሆኑ፣ በአምስቱ ዓመት የአርበኛነት ዘመን ፋሽስት ጣሊያን «ዐማራ» ብሎ ሰይሞት የነበረው ክልል አንድ የዐማራ ግዛት እንዲሆን፣ የቀሩት አካባቢዎች የፋሽስት ጣሊያንን ክፍፍል መሠረት አድርገው የየራሳቸውን ግዛቶች እንዲመሠረቱ እና በነዚህ አገሮች መካከል ኮንፌደሬሽን ይመሥረት የሚል ነው። የእነዚህ ጥናቶች ግብም ከወዲሁ ኢትዮጵያዊው የኢትዮጵያን መፍረስ አይቀሬነት እንዲለማመደውና «ድሮም ተብሎ ነበር» በማለት የአገሩን መፍረስ በፀጋ እንዲቀበል የሥነ- ልቦና ሰለባ ከወዲሁ መሠራቱን የሚያመለክቱ ናቸው።

ካርታ፦ ለወደፊቱ «የትግራይ ሪፑብሊክ» ተብሎ በትግሬ-ወያኔ የሚገነጠለው የኢትዮጵያ አካል በአረንጓዴ ቀለም የተቀለመው ነው።

የትግሬ-ወያኔ እና ዕኩይ ዓላማው ኅልው ሆነው የሚዘልቁት ኢትዮጵያውያን ሠፊውን ለቀን ጠባቡን፣ ኢትዮጵያዊነትን ትተን ጎሣዊ ማንነትን ስንላበስ፣ ዕውነትን ከድተን ከውሸት ጎራ ስንሰለፍ፣ ዘላቂውን ትተን አላቂውን እና ጠፊውን ስንይዝ፣ አኩሪውን ትተን ነገ የሚያሳፍረውን ስንከተል፣ ለኅሊና ሳይሆን ለጥቅም ስንገዛ ነው። እስካሁን የትግሬ-ወያኔ ያለ ልጓም የጋለበን በነዚህ ምክንያቶች ብቻ ነው። አሁን ግን የትግሬ-ወያኔ አጥፍቶን ሊጠፋ ከመጨረሻው ጠርዝ ላይ ቆሟል። የመጥፋቱም ያለመጥፋቱም ጉዳይ የሚወሰነው በእኛ ብቸኛ ምርጫ ነው። ምርጫችን በኢትዮጵያዊነታችን መቀጠል ከሆነ፣ ወያኔ ያጠመደልንን የመነጣጠል መንገድ ትተን በአንድነት በመቆም ኢትዮጵያን ከመጥፋት ለመታደግ ቁርጠኛ አቋም ልንይዝ ይገባል። ቢመሽም፣ እጅግ ብንዘገይም፣ ፈጽሞ ከመቅረት ይሻላል እና እጅ ለጅ ተያይዘን አገራችን እንድናድን ሞረሽ ወገኔ የዐማራ ድርጅት ጥሪውን ያቀርባል።

ከሁሉም በላይ የትግሬ-ወያኔ ወደ መጨረሻ እርምጃው ሲያመራ አጥፍቶ የሚጓዘው፣ ከጽንሱ ጀምሮ በአውራ ጠላትነት ፈርጆ ላለፉት ፵(አርባ) ዓመታት ባገኘው አጋጣሚ ሁሉ ሲገድለው፣ ሲያስረው፣ ሲያሰቃየው እና ሲያሳድደው የኖረውን ዐማራ እስትንፋስ ሳያቋርቋጥ ከጉሬው እንደማይገባ አውቀን፣ ከተደገሰልን ጥፋት እራሳችን መከላከል እንድንችል ከምንጊዜውም በላይ ነቅተንና ተደራጅተን ኅልውናችን ለማስጠበቅ ቁርጠኛ ሆነን እንድንቆም ሞረሽ-ወገኔ አደራ ይላል።

ዐማራን ከፈጽሞ ጥፋት እንታደጋለን!
ፈለገ አሥራት የትውልዳችን ቃል ኪዳን ነው!
ኢትዮጵያ በጀግና እና ቆራጥ ልጆቿ መስዋዕትነት ታፍራ እና ተከብራ ለዘለዓለም ትኖራለች!


ከመላው አገሪቷ በአንድ ቀን፣ በአንድ ፊሽካ ጥሪ፣  የአንድነት ጉባኤተኞች ተሰባስበዋል

0
0

(ዘ-ሐበሻ) “አንድነትን ለመታደግ ከየአቅጣጫው እየተመመ ያለው የአንድነት የሰላማዊ ትግል ሰራዊት፣ በጊዜ በዋናው ጽ/ቤት ከትመዋል፤ ይሄው ታሪክ ሊሰራ፣ የምርጫ ቦርዱ አሳፋሪነት፣ የስርዓቱ ሽፍትነት ሊመሰክር፤ ይህን የአንድነት ልጆች ተጋድሎ ለልጅ ልጅ ሊነግር ታድመዋል።

unnamed (1)ይህ ትልቅ ታሪክ ሲፈፀም በቦታው ተገኝቼ ለመመልከት በመቻል ኩራት ነው የሚሰማኝ”  ሲሉ አስተያየታቸዉን የሰጡት የአንድነት ተጠባባቂ የሕዝብ ግንኙነት ክፍል ሃላፊው አቶ አስራት አብራሃ፣   ነገ እሁድ በሚደረገው ጠቅላላ ጉባኤ፣  አባላት፣  በአራት ቀናት ጥሪ ፣ በቁጭትና በቁርጠኝነት፣  በልባቸው የነጻነትን ደዉል እያቃጨሉ መምጣታቸው እንዳኮራቸው ይናገራሉ።

 

“በአሁኑ ሰዓት ከመላ ሀገሪቱ በአንድ ቀን፤ በአንድ ፊሽካ ጥሪ የአንድነት ጉባኤተኛ አንድነት ፓርቲን በኢህአዲግ ከሚመራው ምርጫ ቦርድና ተላላኪ ወንበዴዎች ሴራ ለመታደግ ብሎም ቀጣይ የትግሉ ምእራፎች ላይ ለመምከር በአሁኑ ሰዓት በአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ዋና ፅ/ቤት ከተን ገብተናል” ሲሉ አንድ የአንድነት አባል አስተያየት ሲሰጡ ፣ ሌላው አባል ደግሞ  “ከተቋቋመበት ጊዜ አንስቶ አንድም ነፃና ፍትሀዊ ምርጫ አስፈፅሞ የማያውቀው የኢትዮጵያ ምርጫ ቦርድ፣ ኢህአዴግ ምርጫ እንዲያጭበረብር በመፍቀዱ ሳቢያ ምርጫን ተከትሎ በሚነሱ አለመግባባቶች በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎች ደማቸው በየመንገዱ ፈሷል፡፡ ምርጫ ቦርድ ከገዳዮቹ ባልተናነሰ የእነዚህ ውድ ኢትዮጵያውያ የደም እዳ አለበት፡፡ ያለጥርጥር የምርጫ ቦርድ ሀላፊዎችም ከገዢው ቡድን ሹማምንት እኩል የደም ዕዳቸውን የሚያወራርዱበት ቀን ሩቅ አይሆንም፡፡” ሲሉ ምርጫ ቦርድ እያደረገ ባለው ነገር በታሪክ ተጠይቂ እንደሚሆን ገልጸዋል።

unnamed

“ምርጫ ቦርድ እየተባለ የሚጠራው የኢህአዴግ ተቀፅላ ተቋም አጅግ አስደማሚ ጠቅላላ ጉባኤ ባካሄድን ማግስት በአራት ቀናት ውስጥ ሌላ አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤ ጠርታችሁ እንደገና ፕሬዚደንቱ ካላስመረጣችሁ የመጨረሻ እርምጃ እወስዳለሁ በማለት ሱሪ በአንገት በሆነ ሁኔታ በድጋሚ ሌላ አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤ እንድንጠራ ተገደናል፤ የጠቅላላ ጉባኤ አባላት ከየቦታው ከአራቱም የሀገሪቱ አቅጣጫዎች ክተት ብለው ሌሊትና ቀን ተጉዘው ፓርቲያቸው ለማዳን በጊዜ ደርሰናል” ሲሉ አንድ ሶስተኛ አባል ይናገራሉ።

 

ምርጫ ቦርድ ሕግ በሚጠይቀው መሰረት ታዛቢዎች እንዲልክ ደብዳቤ ቢደርሰውም፣ ራሱ ባደራጃቸው በነአየለ ስምኔህ፣ ዘለቀ ረዲ ቡድን “ሌላ ጠቅላላ ጉባኤ ተጠርቷል” በሚል እንደማይገኝ በደብዳቤ አሳውቋል። ሆኖም የአንድነት አመራር አባላት “ምርጫ ቦርድ ተገኝም፣ አልተገኝም፣ ጠቅላላ ጉባዬያችንን እናደርጋለን።  በድጋሚ እንደገና ከቀበና ጽ/ቤታችን የዲሞክራሲ፣ የለወጥና የነጻነት ደዉል እንደዉላለን” ሲሉ በአገር እና ከአገር ዉጭ ያለው ኢትዮጵይዊ ሁሉ በዚህ ወሳኝ ወቅት ከጎናቸው እንዲሁን ጥሪ አቅርበዋል።

 

“በዚህ ስርዓት ስር ለአንድ ሌሊት እንኳ ቢሆን በሰላም ተኝቼ ካደርኩኝ ቀኜ ይረሳኝ፤ የረገጠኩት መሬት ይክዳኝ” እንዳሉት የአንድነት የሕዝብ ግንኙነት ክፍል ሃላፊው አቲ አስራት አብርሃ፣ በአንድነት አመራሮች፣ አባላትና ደጋፊዎች ዘንድ ትልቅ ቁርርጠኝነትና ወኔ እየተያ እንደሆነ የሚደርሰን ዘገባ ያመለክታል።

 

እሁድ ለሚደረገው የጠቅላላ ጉባኤ ከመላው አገሪቱ እየተመሙ የመጡ የአንድነት ተወካዮች በአንድነት ጽ/ቤት

 

 

 

የአንድነት ጥር 3 ቀን ጠቅላላ ጉባኤ ላይቭ ዘገባ

0
0

(ሳተናው) የአንድነት ፓርቲ ጠቅላላ ጉባኤ በጥሩ ሁኔተ እየቀጠለ ነው። ምርጫ ቦርድ ሕጉ በሚጠይቀው መሰረት ጠቅላላ ጉባኤ ለመታዘብ አልተገኘም።
አቶ አለነ ማጸንቱ አቶ በላይ ፍቃዱን ኢንዶርስ አደርገው ራሳቸው ከ እጩነት አወጥተዋል። ምርጫዉ በአቶ ዳግማዊ ተሰማና በአቶ በላይ ፍቃዱ መሃከል ነው የሚደረገው።

10394814_759966304088306_449840067842230969_n 10428627_759966307421639_3753389504227116176_n 10906498_759966310754972_3457821015692444450_n

የአንድነት ፓርቲ ዛሬ ጥር 3 ቀን ጠቅላላ ጉባኤዉን ያደርጋል።  ምርጫ ቢቦርድ ከሕግ ዉጭ አንድነት ፓርቲ የሚወዳደርበትን የምርጫ ምልክት አልሰጥም በሚል፣ አንድነትን ከምርጫዉ ለማስወጣት ደፋ ቀና እያለ ነው። የአንድነት ፓርቲ ግን ምርጫ ቦርድ ያስቀመጠውን መሰናክል ለማለፍና ለምርጫ ቦርድ ቀዳዳዎችን ሁሉ ለመዝጋት በሚል ነው ስብሰባው የተጠራው። በዚህ ጠቅላላ ጉባኤ ምርጫ ቦርድ እንዲገኝ ጥሪ የቀረበለት ቢሆንም ሌሎች ግለሰቦች ጠቅላላ ጉባኤ ተጠርቷልና በሁለት ስብሰባዎች መገኝት አንችልም በሚል  ታዛቢ እንደማይልኩ በደብዳቤ ገልጸዋል። ሆኖም የአንድነት ፓርቲ ምርጫ ቦርድ ኖረም አልኖረም ጠቅላላ ጉባኤዉን እንደሚያደርግ በመግለጽ ለምርጫ ቦርድ ምላሽ ሰጥቷል።

12፡30 PM  አዲስ አበባ ሰዓት

በአንድነት የጠቅላላ ጉባኤ ስብሰባ ምርቭጫ ቦርድ በሕግ ታዛቢ የመላክ ግዴታ ነበረበት። ሆኖም ምርጫ ቦርድ ታዛቢ አላከም።  በሕወሃት የተሰተዉን አንድነትን የ”ማገድ” የፖለቲክ ዉሳኔ ለማስፈጸም የቆረጠ ይመስላል።

12፡00 PM  አዲስ አበባ ሰዓት

አቶ ዳግማዊ ተሰማ፣ የኦዲትና ኢንስፔክሽን ሰብሳቢ የነበሩ ሲሆን፣ ከሰብሳቢነታቸው ሪዛይን አደርገው ራሳቸውን ለሊቀመንበርነት ራሳቸው እጩ አድርገው አቅርበዋል። “እኔን ብትነርጡኝ አንድነት የበለጠ ትልቅ ደረጃ እንዲደርስ ለማድረግ እሰራለሁ።ኔን ብትመርጡኝ “በተሻለ አደረጃጀት ከተፎካካሪ በተሻለ ሁኔት ልመራ እችላለሁ” ሲሉ ጉባዬተኞች ድምጽ እንዲሰጧቸው ጠይቀዋል።  ሶስት እጩዎች ቀረበው  ፣ አንዱ አቶ አለነ አቶ በላይን ኢንዶርስ በማድረጋቸው፣ የቀሩት ተወዳዳሪዎች አቶ ዳግማዊ ተሰማና አቶ በላይ ፍቃዱ ናቸው።

dagi

11፡30 AM አዲስ አበባ ሰዓት

አቶ አለነ ማጸነቱ ንግግር እያደረጉ ነው። አንድነት ከሌሎች ፖለቲካ ፓርቲዎች ጋር በመተባበር ትግሉን እንደሚያሳድጉ ተናግረዋል። ምሁራን ወደ ትግሉ እንዲመጡ ትልቅ የማግባባት ሥራ እንደሚሰሩ  ተናግረዋል።  አቶ አለነ ስለ አት በላይ እየተናገሩ ነው። አቶ በላይ ያደረጉት አስተዋጾ  በመጠቀስ ፣ “እኔን ለመምረጥ ያሰባችሁ አባላት በላይ በፍቃዱን እንድትመርጡ እርሳቸውን ኢንዶርስ አድርጊያለሁ” ብለው አቶ በላይን ኢንዶርስ አድርገዋል። አስመራጭ ኮሚቴ ሌላ እጩ ካለ መቅረብ እንደሚችል በገለጹት መሰረት አንድ አባል “የድርጅት ጉዳይ ማምለካ አሰገብቼ ነበር። ” በሚል አቤቱታ አቅርበው፣ የ እጩነት ፎርም እየሞሉ ናቸው።

alene3

11፡30 AM አዲስ አበባ ሰዓት

የአንድነት ፕሬዘዳንታዊ ምርጫ ሊደረግ ነው። አስመራጭ ኮሚቴ ተመርጦ ቦታዉን ይዟል።  አስመራጭ ኮሚቴው ለፕሬዘዳነት ምርጫ በብሄራዊ ምርጫ   የተቀመጡ መመስፈርቶችን አነበቡ። በመስፈርቱ መሰረት ማንኛውም አባል ራሱን እጩ ማድረግ እንደሚችል አስመራጭ ኮሚቴ ለጠቅላላ ጉባኤ ራሱን እጩ አድርጎ እያቀረበ ነው። ሁለቱ አባላት ራሳቸውን እጩ አድርገው አቅርበዋል። አቶ በላይ ፍቃዱ እና አቶ አለነ ማጸንቱ እጩ ሆነው ቀርበዋል።

አቶ በላይ ፍቃዱ ንግግር እንዲያደረጉ በመርጫ ቦርድ ተጠይቀው መናገር ጀምረዋል። አንድነት ባለፊት ሲስት ወራት በ   ከ15 ብቢሮዎች በላይ እንደተከፈቱ፣ በአጠቃላይ አሁን ወደ 30 ቢሮዎች እንዳሉት ገልጸዋል።  የትግሉ ንቅናቄ በቢሮውች እንዲመሩ እናደርጋለን ብለዋል አቶ በላይ። “ምርጫ 2007 ፖለቲክ ለዉጥ ካልመጠ መቼም አይመጣም፣ ለዉጥ እንዲመጣ ከናንተ ሆነ መደረግ ያለበት እናደርጋለን” ሲሊ ለጉባየተኞቹ አስረድተዋል።

5 (5) - Copy

11:00 AM አዲስ አበባ ሰዓት

ዲፕሎማቶች አንድነት በጠራው ጠቅላላ ጉባኤ ተገኝተዋል።  “የአንድነት አባል በአንድ ፌሽካ በአንድ ቀን መገኘት ይችላሉ!” የተከበሩ አቶ ግርማ ሰይፉ

10897929_1561877107393238_227374864912635223_n 1441466_1561877010726581_7637902554378791076_n

10፡30 AM   አዲስ አበባ ሰዓት 

ተወካዮች ቦታቸውን ይዘዋል። የድርጅቱ ሊቀመንበር አቶ በላይ ፍቃዱ መቀመጫቸዉን ይዘዋል። ከክፍለ ሃገር የመጡ በርካታ የጠቅላላ ጉባኤ ተወካዮች የተወሰኑቱ በዚህ መልክ ነበር  በአንድነት ጽ/ቤት ውጁስጥ ያደሩት።

 

የኢትዮጵያውያን ነፃነት ለማስመለስ እስከደም ጠብታ ለመክፈል የተዘጋጀ የአንድነት አባል ውርጭና ብርድ አይበግረውም!!!

ለነዚህ የኢትዮጵያ ልጆች ክብር ይገባቸዋል!!

እነዚህ በፎቶው ላይ የምትመለከቷቸው የአንድነት ጉባኤተኞች ከመላው የኢትዮጵያ ክልሎች በአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ላይ በገዢው የኢህአዲግ መንግስትና በማደጎ ልጁ የምርጫ ቦርድ እንዲሁም ህሊናቸውን በገንዘብ ሽጠው አንድነትን ለመፈረካከስ ከተነሱ ጥቂት ሆድ አደር የማፊያ ቡድኖች እየተሰነዘረበት ያለውን ተከታታይና እልህ አስጨራሽ ደባ ለማክሸፍ በ24 ሰዓት ጥሪ ከሞቀ ቤታቸው ወጥተው፤…… በአንድነት ፅ/ቤት በ03/05/07 ዓ.ም የሚካሄደውን ጉባኤ ለመታደም የአንድነት የክተት ጥሪ ቆራጥ ታጋዮች ናቸው፡፡ ….በፎቶዎቹ ላይ እንደምታዩት እነዚህ የኢትዮጵያን እጣ ፈንታ ለመወሰን በመታገል ላይ ያሉ ሰላማዊ ታጋዮች፤ ……ቁርጥራጭ ወረቀትና ማዳበሪያ አንጥፈው፤…… ድንኳንና ማዳበሪያ ለብሰው፤….በቀዝቃዛው የአድስ አበባ አየር የሲሚንቶ ወለል ላይ በብርድ የሚጠበሱ ቆራጥ፤ለለውጥ የተነሱና ለኢትዮጵያውያን ክብር ከሞቀ ቤታቸው ወጥተው ውርጭ የሚጠጡ፤……ኢህአዲግን እንቅልፍ አሳጥተው የሚያቃዡ ጀግኖቻችን ናቸው!!! ……በእውነት ሁሉም ሀገር ወዳድ ኢትዮጵያዊ ክብር ሊሰጣቸው ይገባል፡፡
==================
በኢትዮጵያውያን ህዝቦች ገንዘብ የኢህአዲግ ካድሬዎች በሊሙዚን መኪና እየተንፈላሰሱ፤……በአለም ላይ እጅግ የቅንጦት ሂወት በሚባል አኳኋን እየኖሩ፡፡ ……ውስኪና ቮድካ ጨብጠው ለቅጥረኞቻቸው በሚያስተላልፉት ቀጭን ትእዛዝ እልፍ የነፃነት አርበኞችን እያስገደሉ፤እያሳሰሩ፤እያሰደቱ…… በህዝብ ሀብት በሚንቀሳቀሰው የህዝብ ሚዲያዎች በቅንጦት ብቅ እያሉ የፍትህና ዴሞክራሲ ተረጋግጧል፤….ሀገሪቱ በሁለት ዲጂት አደገች….ምናምን እያሉ የሚደሰኩሩ አንባገነን የኢህአዲግ ባለስልጣናት ባሉበትና የኢትዮጵያውያንን ነፃነት በጠብ መንጃቸው ቁጥጥር ስር ያረጉትን ኢህአዲጋውያን፤…..ለመታገል ክብርና ነፃነታችንን ከአፈሙዛችሁ ስር ፈልቅቀን እናወጣለን ብለው በውርጭ ለሚጠበሱት የአንድነት አባላትና አመራሮች ስለእውነት የሚያስብ ሁሉ ክብርና አድናቆት ሊሰጣቸው ይገባል!!! ……ውድ የኢትዮጵያ እውነተኛ ልጆች!!! ….እመኑኝ አንድነትን ሊያቆመው የሚችል ሀይል የለም፡፡ ….የምንታገለው ምርጫን የመጨረሻ የትግል ሂደት አድርገን አይደለም፤…. በመሆኑም በነዚህ ብርቅዬ ታጋዮች ስም አንድነት ፓርቲ በተከታታይ ለሚወስናቸው ፖለቲካዊ ውሳኔዎችና የትግል ጥሪዎች አጋርነታችሁን እንድታረጋግጡ መልእክቴን አስተላልፋለሁ፡፡ ……በ2007 ኢህአዲግ የፈራው ለውጥ አይቀሬ ነው፤….ድል የህዝብ ይሆናል!!! ….ለለውጥ እንነሳ!!!

udjj1 udjj2 udjj3 udjj4 udjj5 udjj6

በቂሊንጦ የሚገኙ የአንድነት ፓርቲ አመራሮች ስቃይ እየደረሰባቸው መሆኑን አስታወቁ

0
0

በቂሊንጦ የሚገኙ የአንድነት ፓርቲ አመራሮች ስቃይ እየደረሰባቸው መሆኑን ገለፁ፡፡

Jailበቂሊንጦ ከሚገኙት የአንድነት ፓርቲ አመራሮች መሃል የአንድነት ፓርቲ ህዝብ ግንኙነት ሀላፊ አቶ ሀብታሙ አያሌው እና የድርጅት ጉዳይ ምክትል ሀላፊ የሆኑት አቶ ዳንኤል ሺበሺ ለአዲሱ የአንድነት ፓርቲ ፕሬዝዳንት አቶ በላይ ፍቃዱ ድጋፋቸውን መስጠታቸውን ተከትሎ በወህኒ ቤት ውስጥ ከፍተኛ ስቃይ እየደረሰባቸው እንደሚገኝ ገልፀዋል፡፡

አመራሮቹ ስቃይ እየደረሰባቸው የሚገኘው ለአቶ በላይ ፍቃዱ እውቅና ሰተው በሌላ በኩል በአንድነት ስም በተጠራው ጠቅላላ ጉባኤ ላይ ለተመረጡት የፓርቲው ሰዎች እውቅና መንፈጋቸውን ተከትሎ መሆኑን ለማወቅ ተችሏል፡፡

የአንድነት ፓርቲ አመራር የሆኑት አቶ ሀብታሙ አያሌው እና አቶ ዳንኤል ሺበሺ ከሃምሌ 1 ቀን 2006 ዓ.ም ጀምሮ በእስር ላይ እንደሆኑ ይታወቃል፡፡

Source –

Millions of voices for freedom – UDJ

ሰሚ ያጣ ጮኸት ከካርቱም –አጥናፉ መሸሻ

0
0

751sudan1   በመላው አለም ለምትገኙ ኢትዮጽያዊያኖች ሁሉ    ፤ በተለያዩ ግዜያት  ሰብአዊ  መብታችን  ይከበር ዘንድ ፤  ከምድር ሱዳን የሲቃ ጮኸታን ሰምታችሁ  በተቻላችሁ መጠን ትታደጉን ዘንድ ደጋግመን በፁሁፍ አሰምተናል ፤ እንሆ  በአሁኑ ሰአት ወያኔ ከምንግዜውም በላይ በከፋ መልኩ  ፤ ካርቱም ውስጥ  ስደተኛውን አንደተለመደው እያሳፈሰ ፤ ወዳልታወቀ እስር ቤት እያሳወሰደ ይገኛል ፤ በተለይ ጀዋዛት እየተባለ በሚገኘው እስር ቤት ውስጥ ፤ በሸህ የሚቆጠሩ ወገኖቻችን ታጉሮው ይገኛሉ ፤ ከእነዚህም ውስጥ ለልደት ደሮ ለመግዛት ገበያ የሔዱ እህቶቻችን ከነደሮቸው ፤ ልደትን መድሀኒአለም ቤተክርስትያን አክብረው የሚመለሱ ነጭ የለበሱ ወገኖች  እስር ቤቱን ሞልተውታል ፤ በተጨማሪ ዴም እየተባለ ከሚጣረው ሰፈር ውስጥ አንድ ወጣት ሀለፎም አዲሱ ተካልኝ የተባለ የአንገት መስቀሉን በጥሰው መኪና ላይ ጭነው እስር ቤት አጎረውት ይገኛል ፤ መታወቂያ ለማውጣት እድሜው የማይፈቅድ ወጣት ሳይቀር  ያለ አንዳች እርህራሔ አስር ቤት ይገኛል ፤ ይህን ወጣት እንደምሳሌ ተጠቀምንበት እንጅ በርካታ ወጣቶች መኖራቸውን አናሳስባለን;;

ዛሬ አንባገነኑ ወያኔ ፤ በከፍተኛ መረበሸ ውስጥ አንዳለ ፤ እድሜው እያጠረ ፤ የቆመበት መሬት እየከዳው መሆኑን  እንገነዘባለን ፤ ለዚህም ሱዳን ሀገር የሚኖረውን ስደተኛ ፤ ከኤርትራ በኩል ከሚንቀሳቀሱትና ከሌሎች በነፍጥ ከሚታገሉት ጋር ግንኙነት አላቸው ብለው ስለሚየምኑና ፤  እንዲሁም ሰሞኑን በሱዳን አጎራባች አርማጭሆ አካባቢ በተፈጠረው ሁኔታ በመስጋት ፤ ካርቱም የሚኖረውን ስደተኛ ሕጋዊ የሰደተኛ መታወቂያ ፤ በየሶስት ወር የሱዳን መንግስት ሲያድስ የነበረውን፤ ኢትዮጽያዊ ስደተኛ የለም በማስባል ፤ መታወቂያችን ወያኔ ከፍተኛ ገንዘብ በመክፈል መታወቂያ እንዳይታደስ አስደርጎል ፤ ይህም ማለት ፤ የሚፈልጉትን ስደተኛ   በአፈሳ መልክ አፍነው እንዲወስዱ ያስችላቸዋል ፤ ባሳለፈነው ወር የወያኔ ምክር ቤት ያፀደቀወን  በአሸባሪና ወንጀለኛን ስም ስደተኛውን አሳልፍ በመስጠት የተደረገውን የትብብርን ውል ልብ ይሎል ፤ በተጨማሪ ጀዋዛት እየተባለ በሚገኘው እስር ቤት ውስጥ   የታጎሩትን የስደተኛ መታወቂያ የያዙትን እያሳነጠቁ ፤  ወያኔ ከሱዳን መንግስት ጋር በመመሳጠር ፤ አለማአቀፍ የስደተኞችን ህግ በመጣስ ፤ ስደተኛ መብትን በመንፈግ  ሕገ ወጥ በሆነ  አሰራር መታወቂያ አስር ቤት ውስጥ አስገድደው ፎቶ እያስነሱ ስደተኝነትን የማይገልፅ መታወቂያ በመሰጠት ላይ  መሆናቸውን አጥብቀን እንናስገነዝባለን ;;

ባሳለፍነው ወር የወያኔን መሰሪ ተንኮል ማጋለጣችን ይታወቃል ፤ ይኸውም ስደተኛውን ማህበረሰብ ቅጥ ባጣ አፈሳ በማስመረር በወያኔ ሰላዮች አማካኝነት የወያኔ ኢንባሲ ካርቱም ውስጥ በ28/11/2014 ሰላማዊ ሰልፍ አስደርገውል ፤ የሰልፉም አላማ   የኢሳትን ሚዲያ በመጠቀም ፤ ወደ ሀገራች አንግባ የሚለውን መልእክት ለማስተላለፍ የታቀደ ነበር ፤ እነዚህ ሰብአዊ ክብር ያልፈጠረባቸው ቅጥረኞች  በግፍአን እንባ አንዳላገጡ እንረዳል ፤ በተጨመማሪ እነዚህ በደል የበዛባቸው ወገኖቻችን ፤ለጥያቂቸው መልስ የሚያገኙ መስሎችው ተመልሰው ወያኔ ኢንባሲ በሳምንቱ ሔደው ማንም ሳያናግራቸው በመጡበት አኾሖን ተመልሰዋል;;

ውድ ወገኖቻችን ፤ ሱዳን ሀገር ውስጥ የሚደረሰውን በዝምታ የማይታለፍ በደል ከከፈ ደረጀ ከመድረሱ  በፊት ፤ በመላው ዓለም የምትገኙ ለሰብአዊ መብት መከበር የምትታገሉ   አለም አቀፍ ትብብር የፈጠራችሁ ወገኖች ሁሉ ፤ዛሬም ጨኻታችን ጣራ አልባ እንዳይሆን ፤ ለሱዳን መንግስትና ለዩ ኤን ኤች ስ አር በተቀነባበረ መልኩ ሰብአዊ መብታች ይከበር ዘንድ ፤  በሱዳን ሀገር የምንገኝ ኢትዮጽያዊያን ልሳን ትሆኑን ዘንድ  በአክብሮት እንማፀናለን ;;       ባሳለፍነው ወር 2000 ወገኖቻችን  የ ኤች አይቭ ና የሀቢታይትስ በሸተኞች ናቸው ተብለው ፤ ገንዘብ ንብረታቸውን ሳይውሰዱ ከሱዳን ሲባረሩ  አንድም ተቆርቆሪ ዜጋ የነዚህ ግፍአን     ልሳን ሳይሆን በመቅረቱ  ልብን ያደማል ፤   አሁንም ፤ አሁንም ፤ ይኽ የወያኔ ተንኮል በሰፊው ሳይደገም አፋጣኝ ወገናዊ ትብብራችሁን አንጠይቃለን;;

አጥናፉ መሸሻ

“አንዱ ቡድን ሌላዉን ጥሎ ለማለፍ የሚያደርገዉ ግብግብ ዉጤታማ ሊሆን አይችልም”ትንሳኤ ኢህአፓ

0
0

Tensaye
ድር ቢያብር አንበሳ ያስር!

እኛ የትንሳኤ ስብስብ በተለያዩ ጊዜያት በጽሁፍ፤ በሬዲዮ ብሎም በቴለቪዥን መስኮትያለንን አላማ ለኢህአፓ አባላቶችና በተለያዬ ምክንያት ከድርጅቱ ለወጡ እንዲሁም በድርጅቱ ዉስጥ ለመታገል ለሚፈልጉ ታጋይ ኢትዮጵያዉያን ሁሉ በተደጋጋሚ አሳዉቀናል፤ ዛሬም እንደገና ወደፊት ድርጅቱን ለማጠናከር ተገቢ ናቸዉ ብለን ለምንመኛቸዉና አጥብቀን ስለምንታገልለት ዴሞክራሲያዊ አካሄድ መተንተኑ ተገቢ ነዉ እንላለን፤፤

አሁንም ቢሆን የኢህአፓ ከሁለት መከፈል እጅጉን አሳዝኖናል፤ አበሳጭቶናልም፤ ይህነዉ የሚባል ወይም መሰረታዊ የሆነ የአላማ፤ የርእዩተ አለምና የራእይ ልዩነት ሳይኖር፤ ብዙ ጓዶች ዉድ ህይወታቸዉን የገበሩበት፤ የቆሰሉለትና የደሙለትን ድርጅት፤ ሃላፊነት በጎደለዉና ከምክንያት ይልቅ በስሜት ተገፋፍቶ፤ በግብር ይዉጣ መልክ ድርጅቱን መከፋፈልና ትግሉን አደጋ ላይ መጣሉ፤ በትንሳኤ ስር የተሰባሰብነዉን ጓዶች አንገብግቦናል አሳስቦናልም፤ ለዚህም ነዉ እራሳችንን አሰባስበንና አጠናክረን በዲሞክራሲያዊ ማእከላዊነት የሚመራና፤ ከሁላም በላይ ለሰፊዉ ህዝብ የበላይነት የሚታገል የጋራ አአንድ ኢህአፓ ለማሰባሰብ ያለምነዉ፤፤
ትንሳኤ የኢህአፓ ልጆች ሲል ከሳሾቻችን እንደሚሉት ለወያኔ ያደረዉን፤ ወይንምየኢትዮጵያን ህዝብ ጥቅም አሳልፎ የሰጠዉን፤ አሊያም መስዋትነት የተከፈለበትን የመብትጥያቄ የረገጠዉን ሳይሆን፤ የህዝብን ችግር የራሱ አድርጎ የተነሳዉን፤ በሃገር ፍቅር ስሜትየተቃጠለዉንና፤ የሰማእታትን የትግል አርማ ለመሸከም የሚፈልገዉን፤ አላማ ጽኑ ታጋይ ማለታችን ነዉ፥ ኢህአፓ ይጠናከር፤ ከዉስጥም ሆነ ከዉጭ ያሉትን እናሰባስብ ስንል፤ እነዚያን ለህይወታቸዉ ሳይሳሱ ከጠላት ጋር በመተናነቅ አኩሪ ታሪክ ያስመዘገቡትን፤ በደማቸዉ ታሪክ የጻፉትን፤ በአጥንታቸዉ የኢህአፓን ሰንደቅ ከፍ አድርጎ ለመስቀል ሲሉእንደወጡ የቀሩትን፤ እሬሳቸዉ በየመንገዱ የተጣለዉን፤ በጅምላ በአንድ ጉድጓድ የተቀበሩትንና ፤የአዉሬ እራት የሆኑትን ጓዶች በማሰብ ነዉ፤፤
ኢህአፓ ተጠናክሮአል፤ አባላቶችም እየበዙ ነዉ፤ በህዝብ ዘንድም ሰርጾ እየገባ ነዉ፤ለምትሉን መልሳችን፤ ቤታችን ኢህአፓ ሲሞቅና፤ ሲቀዘቅዝ የትግል እሳቱም ሲጋይና፤ ሲዳፈን ነበርንበትና፤ በደንብ እናዉቀዋለን፤ በአሁኑ ሰአት ኢህአፓ መከፋፈልና መዳከም ብቻ ሳይሆን፤ በህዝባዊ ትግሉ ይህ ነዉ ሊባል የሚችል አወንታዊ ዉጤት ባለማሳየቱ፤ እታገልለታለሁ ከሚለዉ ህዝብ ጋር መራራቅ ብቻ ሳይሆን፤ ህዝቡም የኢህአፓን እንደ ድርጅት መኖርና መንቀሳቀሱን በመርሳት፤ ኢህአፓ በተባለ ቁጥር ኢህአፓ ደግሞ አለ ብለዉ የሚጠይቁ ብዙዎች ናቸዉ፤ ስለዚህ ያልተደረገዉን እንደተደረገ በማስመሰል፤ የህልም ዳቦ መግመጡን ትተን፤ ድርጅቱን እናጠናክረዉ እናጎልበተዉ ነዉ የኛ ምክር አላማም፤፤
እንዲያዉም እራሱን ኢህአፓ ነን በሚለዉ ቡድንና፤ ተገንጥሎ ወጥቶ እራሱን ኢህአፓ-ዴ ብሎ በሰየመዉ ቡድን፤ እርቅ ሰላም ለማዉረድ በቅርቡ የተሞከረዉ ጥረት ፍሬ ሳያሳይ በመቅረቱ፤ በጉጉት የጠበቅነዉም የአንድነት ትግል መጀመር በመጨናገፉ ቁጭታችን ከፍ ያለ ነዉ፤ ይህ ሙከራ ግዜ የፈጀ ዉጣ ዉረድ የነበረበት ስለነበረ፤ ዉድ ጊዜያቸዉን አጥፍተዉ ድርጅቱን ለማዳን የደከሙትን፤ ከወዲሁ እያመሰገን ይህን ቀና ሃሳብ የደገፉትን አበጃችሁ ስንል፤ ጀርባቸዉን የሰጡትን ግለኞች ደግሞ ሌላ ምንም ማለት አንችልም፤ የሰማእታት አጽም ይፋረዳችሁ ከማለት በስተቀር፤ ይህ እርቀ ሰላም ቢሳካ ኖሮ ኢህአፓን እንደ ድርጅት ከማጠናከሩም በላይ፤ በአሁኑ ሰአት የኢትዮጵያ ህዝብለሚያደርገዉ ጸረ ወያኔ ትግል፤ አጋዥም አበረታችም ይሆን ነበር፤ አለመታደል ነዉ እንዲሉ፤ በአመራር ቦታ ያሉትና፤ እርቅ ሰላሙን የተሳተፉት ጓዶች ቅራኔን ከማርገብ ይልቅ ማፋፋምን፤ ልዩነትን አጥብቦ በጋራ ከመቆም ይልቅ ቃላትን በመሰነጣጠቅ ልዩነትንአስፍቶ በተናጠል መቆማና፤ እንደጠላት መተያየትን መርጠዋል፤ ይህ ከድርጅትና ከጋራ ጥቅም ይልቅ ተክለ ሰዉነትን መገንባት የተጠናወተዉ በሽታ፤ ለድርጅቱ ዉድቀት ብቻ ሳይሆን በኢትዮጵያ ህዝባዊ ትግል ላይም የማይሽር ጠባሳ እንደሚያሳርፍም ጥርጥር የለነም፤፤

የዛሬን አያድርገዉና፤ ትናንትና በኢድሕቅ የትግል ሂደት ዉስጥ መኢሶን ጎን የተሰለፈዉ ኢህአፓ ዘንድሮ በዉስጡ የተፈጠሩ ችግሮችን በዲሞክራሲያዉ ሁኔታ መፍታት፤ ለኢትዮጵያ ህዝብ ትግል ሲባልም ይቅር ተባብሎና፤ ተቻችሎ ትግሉን መቀጠል አለምቻሉ ሁላችንም ያስገረመ ሚስጥር ብቻ ሳይሆን፤ ድርጅቱ ምን ያህል ከዲሞክራሲያዊ አሰራርና ከምንክንያት ጋር እንደተጣላም ያመላክታል፤ ድርጅቱ የራስ ንብረት ይመስል፤ ሌሎችን ድንጋይ ተሸክመዉ ይቅርታ ካላሉ፤ አይናች ሁን ላፈር ማለት፤ አዋቂነትን ሳይሆን አምባገነናዊ ባህሪን የሚያሳይ ነዉ፤ ስለዚህ ኢህአፓ አብቦና አፍርቶ ለማየት የምንፈልግ ሁሉ ነገሩን በአንክሮ ተመልክተን መወያየትና ለችግሮችም መልስ መሻት ተገቢ ነዉ እንላለን፤፤
ለነገሩማ በአመራር ቦታ ብዙ ጊዜ መቆየት ድርጅትን የግል ንብረት አድሮጎ የማየትንአባዜ ያስከትላል፤ ተመክሮአችን ሁሉ የሶሻሊስት ፍልስፍና ሆነና፤ ሁላችንም ከድርጅት የስልጣን ኮረቻ መዉረድን ወይም ለሚገባዉ ሰዉ ስልጣን መልቀቅ ተገቢ ስርአት አድሮጎ መቀበል ተስኖን፤ እንደወያኔዉ አምባገነን መሪ ሞት ካልወሰድን በስተቀር የሙጥኝ ማለቱን ተያይዘነዋል፥ ድርጅቱን የግል ንብረት አድርጎ መቁጠር ብቻ ሳይሆን አንዳንዶቻችን የድርጅት አባላትም ጭምር የመለኮትን ያህል እንዲያመልኩን እንሻለን፤ በቅርቡ ከወያኔ አገዛዝ በራሱ ፈቃድ ጥሎ የወጣዉ አቶ ኤርሚያስ ለገሰ፤ የመለሰ ቱርፋቶች በሚለዉ መጣጥፉ፤ ምን ያህል የወያኔዉ ድርጅት የአቶ መለሰ ዜናዊ የግል ንበረት እንደሆነና፤ አቶ መለሰም በድርጅቱ ላይ የነበራቸዉን ያልተገደበ ፍጹማዊ ስልጣን አመላክቷል፤ ስለዚህ እንደዚህ አይነት በድርጅት ዉስጥ የሚፈጠሩ ግለሰብ አምላኪነትና ያልተገደበ ስልጣን መኖርን፤ ሁላችንም ለዲሞክርሲ፤ ለፍትሕና ለእኩልነት የምንታገል ሁሉ ልናወግዘዉ ይገባል፥ በአመራር ቦታ የሚቀመጡ መሪዎች የስልጣን ጊዜያትና ገደብም እንዲኖራቸዉ የግድ ይላል፤ ድርጅቶችም ይህን በተመለከት ህግ ማዉጣት ብቻ ሳይሆን ለተግባራዊነት መታገል አለባቸዉ፤በድርጅት ዉስጥ የታቀፉ አባላትም፤ ከግለሰብ አምላኪነትና ከቡድንነኝት ነጻ በሆነ መንፈስ ሃላፊነታቸዉን መወጣት ይኖርባቸዋል፤ ማንኛዉን አይነት አምባገነናዊ ባህል ማስወገድና በምትኩ የተለያዩ ሀሳቦች ሊሸራሸሩበትና አባላት ያለምን ስጋት ያላቸዉን ልዩነት ሊያሰሙበት የሚችል መድረክ መፍጠር ተገቢ ነዉ፤፤

የአምባገነን ባህል አሜን ብሎ የተቀበለ፤ ስልጣንን ከሃላፊነትና ከተጠያቂነት ማጣመርየተሳነዉና፤ መመረጥንም ሆነ ስልጣን መልቀቅን ማቀናጀት የማይችል ድርጅት እንኳን ህዝብንና አገርን ነጻ ሊያወጣ ይቅርና እራሱንም ነጻ ማዉጣት አይችልም፤ አጋጣሚ ሰጥቶትም ስልጣን ላይ ቢቆናጠጥ ለህዝብ ነቀርሳ እንጅ መፍትሔ እንደማይሆን ወያኔ በአሁኑ ሰአት በኢትዮጵያ ህዝብ የሚያደርሰዉ ግፍ በቂ ምስክር ሊሆነን ይገባል፤ ስለዚህ የአባላቶች ንቁ ተሳትፎ፤ አዙሮ መመልከትን ብሎም ተላምጦ የተሰጠን ብቻ ከመዋጥ ይልቅ እራስም ማኘክን መልመድ፤ ድርጅትንም ሆነ አገርን ከጥፋት ያድናል፤ አለበለዚያ ግን እነዚያ እንደመልኮት ሲታዩ የነበሩ አመራሮች መምራት ሲያቅታቸዉ ወይም በሞት ሲለዩ ድርጅቱ ሞተሩ እንደተበላሸ ተሽከርካሪ መቆሙ የማይቀር ይሆናል፤፤

ከዚህ ባሻገር በቅርቡ ስለወጣዉ የኢህአፓ-ዴ እና እርማት እንቅስቃሴ ስለ ተባለዉ ቡድን የጋራ መግለጫ በኢንተርኔት ድረገጽ ተመልክተናል፤ በጥቅሉ ጅማሬዉንና፤ ጽንሰ ሃሳቡን የምንደግፈዉ ቢሆንም በ አሰራሩ ላይ ግን ልዩነት አለን፤ በቅድሚያ በጥሪዉ ሆነ በመሰናዶዉ የኢህአፓ ጉዳይ ይመለከታቸዋል የተባሉትን ሁሉ ማሳተፍ ተገቢ ነዉ፤ በተለይም በአሁኑ ሰአት የተለያዩ ቡድኖችም ሆነ ግለሰቦች ኢህአፓን አንድ ለማድረግ በሚንቀሳቀሱበት ጊዜ ከወዲሁ እነሱን ማማከርና በሂደቱ እንዲሳተፉ መጋበዙ ተገቢ ሆኖ እያለ፤ አንዱ ቡድን ሌላዉን ጥሎ ለማለፍ የሚያደርገዉ ግብግብ ዉጤታማ ሊሆን አይችልም፤ ትንሳኤም የተነሳለት አላማ ግብግቡ ቀርቶ ሁሉም ጓዶች በሰከነና አስተዋይነትበተሞላበት ሁኔታ ችግሩን በአንክሮ ተመልክተዉ መፍትሔ ላይ እንዲደርሱና አንድ ኢህአፓን ይዘዉ እንዲወጡ ስለሆነ አላማችን፤ ከወዲሁ አሰራሩ ሁሉንም እንዲያቅፍ እናሳስባለን፤፤
ኢህአፓ በተባበረ ክንዳችን ይጠናከራል፦
የኢትዮጵያ ህዝብ ያቸንፈል፦

ሳዲቅ አህመድ ለዛ ባለው አነጋገሩ ያላደረግናቸዉ ልናደርጋቸዉ የሚገቡ ነገሮችን ይጠቁመናል

0
0

ዳላስ ላይ በተደረገ የኢሳት ገቢማሰባሰብ ዝግጅት ላይ ጋዜጠኛና አክቲቭስት ሳዲቅ አህመድ ለዛ ባለው አነጋገሩ በትግሉ ያላደረግናቸዉ ልናደርጋቸዉ የሚገቡ ነገሮችን ይጠቁመናል:: ያድምጡት – ያተርፉበታል::

ሳዲቅ አህመድ ለዛ ባለው ንግግሩ ያላደረግናቸዉ ልናደርጋቸዉ የሚገቡ ነገሮችን ይጠቁመናል

Video- ማን ያርዳ የቀበረ ማን ይናገር የነበረ

0
0

ማን ያርዳ የቀበረ ማን ይናገር የነበረ

 

Andualem


ህወሃት/ብአዴን በጨለማ ጐንደርን በታንክ ምን ለማድረግ !!?

0
0

የጎንደር ከተማ (ፎቶ ፋይል)

የጎንደር ከተማ (ፎቶ ፋይል)


ነብሮ ከሰ/አሜሪካ

ኢዲዩ በወገራ፤ጎንደርና ጭልጋ አውራጃዎች ኃይሉን አጠናክሮ ወደ ጎንደር ከተማ እየገሰገሰ ይሄድ በነበረበት ወቅት በጎንደር ክፍለ ሀገር የነበረው የደርግ ወታደራዊ አቅም ደካማ ነበር።በኋላ ግን ከየክፍለ ጦሩ በመሳብ ገስጥ በሚባለው ክፍለ ጦር የተካተተ ከፍተኛ የጦር ክምችት ወደ ጐንደር ዘመተ። ከአዘዞ እስከ ብልኮ ጎንደር በደርግ ብረት ለበስና መድፍ በጫኑ የጦር ኃይል ካሚዮኖች ተጨናነቀች።በዚያች ቀንና ሰአት በሕዝቡ ዘንድ የተለያዩ አመለካከቶች ይንፀባረቁ ነበር። ተማሪው አስተማሪው፤ የከተማ ነዋሪውና የመንግሥት ሠራተኛው፤ነጋዴው በኢዲዩ፤በደርግና ኢህአፓ አመለካከት ውስጥ ተከፋፍሎ ሲመሽግ እንደነበር የአይን እማኝ ሆኜ መናገር እችላለሁ።በወገራና ጭልጋ ያመራውን የደርግ ጦር እንቅስቃሴ ለመከታተል አቅሙና ጊዜው ስለአልነበረኝ ከጐንደር ወደ ሁመራ ያቀናውን እንቅስቃሴ ለመከታተል ሁኔታዎች ረድተውኝ ነበርና የሚከተለው ነበር።

ጦርነቱ ከጐንደር ከተማ ወጣ ብሎ የተጀመረ ሲሆን የደርግ ኃይል ከፍተኛ የጦርነት ልምድ ያለው በትጥቅና ወታደራዊ ሎጅስቲክ የተደራጀ ስለነበር በኢዲዩ በኩል የነበረው ሠራዊቱ የጥቂት ጊዜ የጦርነት ልምድና አብዛኛው ሕዝባዊ ሠራዊት በመሆኑ ደርግ አቅም አግኝቶ የላይ አርማጭሆ ወረዳ ዋና ከተማ ትክል ድንጋይን አልፎ መሄድ ጀመረ።ከዚያ በኋላ ግን ደርግ ያላሰበው ሁኔታ ገጠመው። ገና ቆልማሜ ላይ እንደደረሰ የአርማጭሆ የመሬት ቀማመጥ ራሱ ሌላ ጦር በመሆን ደርግን ይፈታተነው ጀመር። ከቆልማሜ እስከ ሙሴ ባምብ የነበረው የደርግ ጉዞ ደርግን ከፍተኛ ዋጋ እንደሚያስከፍለው ሳይወድ በግድ እንዲገነዘብ አደረገው።ደርግ ወደ ሥልጣን ከወጣ በኋላ ብዙም ሳይቆይ የዚያ አይነት ፈተና ሲገጥመው ቆም ብሎ ማስብና የችግሩን መፍትሄ ማፈላለግ ሲገባው ግፋ በለው በማለት ቀጠለ።

ከትክል ድንጋይ እስከ አሸሬ በቀኝና በግራ በኩል ነዋሪ የሆነው የአርማጭሆ ሕዝብ አካባቢያውን በመልቀቅ ቤተሰቡን ከደርግ ጦርና ተወንጫፊ መድፎች በማራቅ የኢዲዩን ጦር በማናቸውም አይነት መተባበርና ማገዙን ቀጠለ። አንድ የገስጥ ክፍለ ጦር አባል የነበረ ሙሴ ባንምብ በጥይት ተመትቶ የነበረ እኔም ኢህአፓ አባላቱን ሲያሰናብት አንዱ ተሰናባች ስለነበርኩ ሁለታችንም በአንድ ክላስ(ክፍል) አብረን መማር ስንጀምር ከቀናት አንድ ቀን ትንሽ ጥያቄዎች አቀረብኩለትና ብዙ ገጠመኞችን አጫወተኝ። ይኸውም የገስጥ ጦር ያከተመለት ሙሴ ባንምብ ነበር።

ነገር ግን በኢዲዩ በኩል አንድ ወጥ አመራር ስለአልነበረ የገስጥ ጦር ባለበት ሆኖ አቅሙን አጠናክሮ የመከላከል ወይም ወደ ኋላ ማፈግፈግ ከሚል ነጥብ ደረጃ ደርሶ እያለ አንድ የገስጥ ጦር ሻምበል ምልክት አሳየ (ባውዛ )አበራ ያ ማለት ወደፊት ግፋ በለው የሚል መልዕክት ነበረ:- ይሁን እንጅ ከአንገረብ ማዶ ጠገዴ ወልቃይትና ጠለምት በቀኝ አርማጭሆ በግራ የገስጥን ጦር እርሳስ እየቀለቡ በመጓዝ ላይ እንዳለ እኔ ኩፉኛ ቆስየ ስልነበር ወደ ክምና ሄድኩ የገስጥ ጦር ግን የሚከፍለውን መስዋዕትነት እየከፈለ ሁመራ ደረሰ ያ ጊዜ በደርግ ታሪክ መጥፎ ገጠመኝ ነበር ብሎ ነበር በአጭሩ የተረከልኝ።

አንድ በውል ያልተመለከትነውና የሚያሳዝነው ነገር ቢኖር ግራኝ መሀመድ ከኢትዮጵያ ተነስቶ ኢትዮጵያን ሲወር የገሰገሰው ወደ ጐንደር ነበር፤ድርቡሽ(መሐዲስት) ከሱዳን ተነስቶ ኢትዮጵያን ሊወር ሲመጣ መጀመርያ ያቀናው ወደ ጎንደር ነበር፤የፋሽስት ጣሊያን ወራሪ ጦር ከኤርትራ በመነሳት በሁመራ አድርጎ የገሰገሰውም ወደ ጐንደር ነበር፤ ዘረኛውና ቅጥረኛው ህወሃትም ብረት ለበስ ታንኮቹን አሰልፎ ከመቀሌ የገሰገሰው ወደ ጐንደር ነው።

በሥነ-ምግባር ብልሹ የሆኑ አስተዳዳሪዎች የሚሾሙት ጐንደር ነው። በሀገር ደረጃ አንዳንድ ፖለቲካዊ ውጥረቶች ሲከሰቱ የሚጠረጠረውና ጣት የሚቀሰርበትም ጐንደሬው ነው።የትምህርት እድልና የደረጃ እድገት እንዳያገኝ የሚደረገው ጐንደሬው ነው።በመጥፎ አርአያነት ቆርጦ ቀጥል ስም የሚለጠፈውም ለጐንደሬው ነው።የህወሃት የመሬት ቅርምት ትኩረትም በጐንደር ነው።በደርግ ጨፍጫፊ ሥርዓት የጥይት ሰለባ የሆነው ጐንደሬው ነው።መንግሥት እገለብጣለሁ ያለው ሁሉ የሚመሽገውና አካባቢውን የጦርነት ቀጠና የሚያደርገው በጐንደር አካባቢ ነው።ይህ ሁሉ ደባ ሲፈፀም የጐንደርን ሕዝብ ድምጽ የሚሰማና ቀና ብሎ የተመለከተው የለም።

እኔ እስከማውቀው ድረስ የጐንደር ክፍለ ሐገር ሕዝብ በኢትዮጵያ ታሪክ ቀዳሚውን ቦታ ሊይዝ እንደሚገባውና ዳር ድንበሩን ያለመንግሥት ኃይል በራሱ አስከብሮ የኖረ ሀገር ወዳድና በኢትዮጵያዊነቱ የሚኮራ ሕዝብ ነው።ይህን ስል አእምሯቸው ነገር እንደ ግራምጣ ለመሰንጠቅ የተፈጠሩ አዋቂ ነን የሚሉ ከጠባብነት ጋር ሊያላትሙት እንደሚከጅላቸው ይገባኛል። የኔ መነሻ ግን እሱ አይደለም ማንኛውም ኢትዮጵያዊ ይህ የዘረኝነት ወረርሽኝ (ቫይረስ)ከመምጣቱ በፊት ክርስቲያን እስላም፤ ትግሬ ኦሮሞ፤አማራ አፋር፤ሀድያ ጉራጌ….ወዘተ ሳይባባል በጀግንነት፤በጋራና በአንድነት የሀገሩን ዳር ድንበር ሳያስደፍር ሉዓላዊነቷን ጠብቆ ያቆየ ሕዝብ መሆኑን ዘንግቼ አይደለም።የጹሑፌ መነሻ ሰሞኑን ህወሃት የትግራይ ሚሊሻዎችን በማስታጠቅ በአማራ ክልል ከሚኖረው የጎንደር ሕዝብ ጋር ለማጋጨት የሰነዘረውን ጦርነት መሠረት በማድረግ እንደ አንድ ኢትዮጵያዊ ዜጋ ለአካባቢው ሕዝብ ድምጽ መሆንና ነገሩን በሰላማዊ መንገድ እንዲፈታ የሁለቱ ክልሎች ሕዝብ አጽዕኖት በመስጠት በተለመደው ባህላዊ የችግር አፈታት ጥበብ የተከሰተውን ችግር እንዲያስወግዱትና ወደ ድሮው አንድነታቸው፤አጋርነታቸው እንዲመለሱና ችግሩን እየገፋ ያመጣውና ጠንሳሹም ህወሃት እንደሆነ እንዲገነዘቡ ለማድረግ ነው።

የድሮዎቹ ደጋግ ወላጆቻችን እንዲህ አይነቱን ጠብ አጫሪነት ሲመለከቱ አትስሙት ** ውሃው ሂያጅ ድንጋዩ ቀሪ ነው ** ይሉት ነበር ሰው(ሕዝብ) ድንጋይ ነው ማለታቸው ሳይሆን በምሳሌያዊ አነጋገር መንግሥት ይሄዳል ሌላ መንግሥት ይመጣል ሕዝብ ግን አይቀያየርም ለማለት ነው። ስለዚህ መንግሥትን ወይንም ማንኛውንም እንደ ህወሃት ያለ ወራሪ እንደ ውሃ ሕዝብን ደግሞ ቀየውን እንደማይለቅ ድንጋይ አስመስለው ይናገሩት ነበር። የአሁኑ ትውልድ በዚያ ምሳሌያዊ ዘዴ የተሞላበት አነጋገር ያምናል አያምንም ብሎ ለመናገር በጣም ይከብዳል።ሆዳምነት ፤አድር ባይነት፤ስግብግብነት የተጠናወተን ዞሮ ማየት የተሳነን የሰውን ሰብአዊነት እንደጨርቅ የምንቦጭቅ፤ተራ በተራ ለግዳይ የምንቀርብ፤ለመተማመን የተቸገርን ትውልዶች ነው በአሁኑ ሰአት ያለነው።

የሠሐራን በርሃ አቋርጦ ወደ ዐረብ አገር በእግር መጓዝ ፤አይከፍሉ ከፍሎ በመርከብ ወደ ዐረብ አገር መንጎድ ሞትን በመፍራት ነው ወይም የኢኮኖሚ ችግርን ለመፍታት ነው። ዳሩ ግን ችግሩን መፍታትም ሆነ ከሞት ማምለጥ እንዳልቻሉ አይተናል። ይህን ጦስ ያስከተለው አሁን ሥልጣን ላይ ያለው የህወሃት ቅጥረኛ ኃይል ነው።ይባስ ብሎም በነዚህ የኢትዮጵያዊነት ዜግነት ባላቸው አብዛኛዎቹ ገና ሕፃናት ወጣቶች ላይ የደረሰውን አስደንጋጭ የሞት አደጋና ሌላ ለመግለጽ እጅግ የሚዘገንኑ ሁኔታዎች ሲፈጸሙ የዓለም ሕዝብ ሳይቀር ከኢትዮጵያውያን ጋር በመሆን ሀዘኑን ሲካፈለን የህወሃት/ኢሃዲግ መሪዎችና አባላት አንድም የተፈጠረ አዲስ ነገር የለም በማለት በአራት ነጥብ ደመደሙ።

ወደዚህ ነጥብ እንድገባ የገፋፋኝ ሞት ካልቀረ ለምን የሚገድለንን እየገድለን አንሞትም?ምናልባት እንዴት እንጀምረው የሚለው ሊያስቸግር ይችል ይሆናል ልቡ ለቆረጠና ለወሰነ ግን ቀላል ነው። መድረሻቸው ይህ ነው ለማለት ባልችልም የከፋው ፤ግፍና በደል የተፈፀመበት፤የዜግነት መብቱ የተገፈፈበት፤ፍትህ ያጣ ኢትዮጵያዊ የህወሃትን ሥርዓት ማስወገድ አለብኝ ብሎ ማመን አለበት። በዚህ ከተማመን ዛሬ ነፍጥ አንስተው እየተፋለሙ ያሉ ተቃዋሚ የፖለቲካ ድርጅቶች ቁጥር የሚናቅ አይደለም ከሚመስለው ጋር ተሰልፎ የጋራ ጠላትን ታግሎ መጣል ይቻላል።

ህወሃቶችና አጋፋሪዎች፦እንድታውቁት የሚያስፈልግ ነገር ቢኖር የአክሱምን ሥርዎ መንግሥት የደመሰሰችው ዩዲት ጉዲት እንጅ የጎንደር ሕዝብ አይደለም። የጎንደር ሕዝብ እንደ ግራኝ መሐመድ፤ጣሊያን፤ድርቡሽና ህወሃት ግፍ አልፈፀመም። የሌላውን አገር ወይም አካባቢ ሊወር አልተነሳም ይልቁንስ በደም በተቦካ አጥንቱ ድንበሩን ጠብቆና አስከብሮ የመንግሥት ግብር ገብሮ የኖረ ጎንደሬ ሆኖ በኢትዮጵያዊነቱ እጅግ የሚኮራ ሕዝብ ነው የጎንደር ሕዝብ ።

አይን ያማረውን ሁሉ የራስ ለማድረግ በሚቋምጥ ስግብግብ አስተሳሰብና ቀሽም ብልጣ-ብልጥነት ጥቂቶች ብዙዎቹን አጭበርብረው ሊሳካላቸው የሚችለው አንድ ጊዜ ብቻ ነው።ከዚያ በኋላ ያለው ባለቤቱ እንጉልቻም ካልሆነ ፈላጊው ቢሞክርም በል ተመለስ ድንበሩ እሱ ነው ብሎ ባፍ ጢሙ እንዲደፋ ማድረግ ይቻላል።የወልቃይት ጥገዴ የአርማጭሆ፤የጠለምት ፤ አዳኝ አገር ጫቆ እና የጎንደር ሕዝብ በቅርቡ ያደረገው ይህንኑ ነው። ይህም ተጀመረ እንጅ የመጨረሻው አይደለም። እንዲያ ነው የአገሬ ሕዝብ!! ሽንፋ ፤ቋራ መተማ፤ጭልጋ፤አለፋ ጣቁሳ፤ደምብያ፤ጠዳ፤በለሳ፤ሰሜን፤አምባጊዮርጊስና ዳባት፤አዳርቃይ፤አዲሰላም፤በየዳ ጃናሞራና በለሳ ይዞህ ብቻህን አይደለህም በርታ።ከጎንህ የምንሰለፍበት ቀን ሩቅ አይደለም።

በመጨረሻም ለህወሃት የመከላከያ ሠራዊት ጥብቅ ማሳሰቢያየ ይድረስ፦አሁን እየገደልከው ካለው ሕዝብ አብራክ መፈጠርህን የምትክድ አይመስለኝም። በተግባርህና በአስተሳሰብህ ግን ክህደትህን አጉልቶ የሚያሳይ በርከት ያሉ ማስረጃዎችን ከአራቱም ማዕከል እየመዘዙ ማቅረብ ይቻላል።አለቆችህ ዛሬ ባለፎቅ፤ባለ ዶላርና የተንደላቀቀ ኑሮ እየኖሩ እንዳሉ ታውቃለህ።ይህን አይነት የደላ ኑሮ ለመኖር አንተ ህዝብን በጅምላ መፍጀት ይገባሃል ወይ?የዛሬዎቹ ጌቶችህ ይህ አሁን የመሣሪያህን አፈሙዝ አዙረህ በምትገድለው ህዝብ ከዚህ እንደ ደረሱ በግልጽ ልነግርህ እወዳለሁ።ሰፊ ዘገባ ይዥ እስከምቀርብ ለዛሬ ያለኝ መልእክት ህወሃት ከፊትህ ለህዝብ ነፃነት ከሚፋለሙ ጀግኖች መሣሪያ የሚተፋው እርሳስ ከኋላህ ህወሃት ያሰማራው ገዳይ ኃይል በሚተኩሰው ጥይት ጀርባህንና ግንባርህን እየተመታህ የአሞራ ቀለብ ከመሆን ራስህን በራስህ ልትታደገው ይገባል።እንደ ድሮው ቤት ያፈራውን አካፍሎ የታመመ አስታሞ የቆሰለን እስኪያገግም ሸሽጎና የሞተን እየቀበረ መውጫ መግቢያውን እየመራህ የሚሄድ ሕዝብ የለም።ያለህ አማራጭ የህዝቡን ትግል መቀላቀል ወይም የሰው በላው ሥርዓት ማገዶ በመሆን ማለቅ ብቻ ነው። የአገር መከላከያ ሠራዊት ሳይሆን የህወሃት የእድሜ ዘመን እንዲረዝም የሕዝብን መብት በማፈን ተግባርህ መቀጠል አይገባህም።ዛሬ ብዙ አማራጮች አሉህ።እነዚህ አማራጮች ሳይጠቡ ተጠቀምባቸው ለኢትዮጵያ ሉአላዊነት ከሚዋደቁት ጎን ተሰለፍ፤የሕዝብ ልጅ በመሆን ታሪክ ሥራ ።
ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!!!

የማለዳ ወግ …የኢትዮጵያ አፈር የጠራው ጠቢብ የክብር ጉዞ ፍጻሜ !

0
0

መልካም ስም ከመቃብር በላይ ይውላል …!

image-9d7f88cbdecd3715a84ff1e923f19a265e6c 3ebc9096e18394f23acdc537c8db-V_resized_1አርአያነታቸው ፋና ወጊ ሆኖ እያለ ብዙ ያል ተነገረላቸውን ዶር በርናርድ ብሬድሊ አንደር ሰንን ባዘከርኩበት የማለዳ ወጌ የጠቢቡን ህይዎት ከጃማይካ እሰከ አሜሪካ ለመቃኘት መሞከሬ እውነት ነው ። ዛሬም የምቀጥለው ከዚያ ለጥቆ ያለውን የዶር በርናርድን አፍሪካና ኢትዮጵያ ያደረሰውን መንገድ ሲሆን እንደ መግቢያ በአንድ የጥምቀት ዋዜማ ጎንደር ከዶር በርናርድና ከባለቤታቸው ከሲስተር እማዋይሽ ገሪማ ጋር የነበረንን አጭር ቆይታ በጨረፍታ በመቃኘት መጀመሩን ልቤ ፈቅዷል … የፈቀዳችሁ ተከተሉኝ !

ጎንደር በጥምቀት ዋዜማ …

ባልሳሳት ወርሃ ጥር 2004 ዓም ይመስለኛ ል … ጥምቀትን በጎንደር ለመታደም ሲገሰግስ የሚመጣ አውቶቡስ በአባይ በርሃ ተገልብጦ ተሳፋሪው በማለቁ ጎንደርና ጎንደሬው ማቅ ለብሰው ፣ አዝነው ተክዘዋል … ምክንያት አላቸው ፣ ምክንያቱም ከጎንደር ጥምቀት ክብረ በአል ጋር የቴዎድሮስ ሃውልት ምረቃ ሊከበር በዝግጅት ላይ እያለ ከወደ አባይ በርሃ የተሰማው መርዶ የከፋ ነበርና ነው ። መርዶው በመይሳው ካሳ ሃውልት ምረቃና በጥምቀቱ የደመቀ ዋዜማ ስሜታቱ በደስታ ላይ የነበርነውን በአል አክባሪ ሁሉ ቅስም የሰበረ ነበር። በርሃው ወገኖቹን በልቶታልና ፣ ጎንደሬውን አንገቱን በሃዘን ደፍቶ ማቅ ያለበሰው ቀን ቢኖር ይህ ቀን ነበር። ደስታቸውን ለመግለጽ ሳግ እየተናነቃቸው ለቴዎድሮስና ለሚናፍቋት አንድነቷ የተጠበቀች ኢትዮጵያ ያላቸውን ፍቅር በመግለጽ ላይ የነበረው ኢትዮየጵያዊ ከትንሽ እስከ ትልቅ በርሃው በበላቸው ወገኖቹ በሃዘን ቅስሙ መሰበሩና ስሜቱ መጎዳቱን በእያንዳንዱን ፊት ይነበብ እንደነበር አይረሳኝም …

በአባይ በርሃ ገደል ገብቶ ሰው የጨረሰው አውቶቡስ እኔ ፣ ልጆቸና እህቴ በአንድ ሆነን በተሳፈርንበት አውቶቡስ እኩል ከአዲስ አበባ ነበር የተነሳው። ከአዲስ አበባ እስከ አባይ በርሃ ድረስ ከበስተኋላችን ይጓዝ ነበር ። በአባይ በርሃ ደልደል ባለ መንገድ ዳር በአንድነት ለደቂቃዎች እረፍት አድርገንም ነበር ። እኛ ቀድመን አቀበቱን ወጠን ደጅን እንደደረስን ፣ የማይታመነውን አደጋ መርዶ ሰማን… ይከተለን የነበረው አውቶቡስ ከሃምሳ በላይ አብዛኛው እንደኛ ጥምቀትን በጎንደር ሊያከብር የተሳፈረው ወገን ገደል ገብቶ ሰው አንዳለቀ በቀትር የራዲዮ ዜና እወጃ ሰማን! ያ ቀን ለእኔ የሚረሳ እና የሚዘነጋ አይደለም ! በአባይ አፋፍ አንድ ጫፍ እረፍት ባደረግንባት ደቂቃ ሰላምታ የተለዋወጥኳቸውን ወገኖች በሰአታት ልዩነት የማለቃቸውን አሰቃቂ ዜና የሰማሁባት እለት ሆዳችን ተላውሶ አዝነን ከፍቶን ነበር ጎንደር በጥምቀት ዋዜማ የገባነው …

ሃዘን የጎዳው ጎንደሬ ግን በሃዘን ልቡ ተሰ ብሮም ቢሆን ሽርጉዱ ከጓዳ እስከ አደባባይ አድርቶታል። ጎንደሬው ከዘመድ አዝማዶቹ አልፎ ተርፎ ” ኑ በጥምቀት ኢትዮጵያን ተመል ከቱ ! ” በሚል እንግዳ ተጠርቷልና ሃገሬው እን ግዶቹን ሊቀበል ከጓዳ ጥንስስ እስከ አደባባይ ከተማ ማስዋብ ዝግ ጅት ተጠምዷል … ደግ ሞም ወቅቱ የቋረኛው አጼ ቴወድሮስ ሃውልት የሚመ ረቅበት ልዩ አጋጣሚ ሆኖ ተገጣጥሟ ልና አጋጣሚው መሪር ሃዘን እያዘኑ መሳቅም ከመሆን ጋር ተደባልቋል …

የዶር በርናርድ ባለቤት ፣ የታዋቂው አርበኛ ደራሲ ገሪማ ታፈረ ልጅ ፣ ወይም የታዋቂው የፊልም ደራሲና የታሪክ ተመራማሪ የፕሮፊሰር ኃይሌ ገሪማ እህት ሀገር ወዳዷ ትጉህ እመቤት ከሲስተር እማዋይሽ ገሪማ ጋር በየተናኘነው በዚህ በጨነቀው የጥምቀቱ ዋዜማ ነበር ። ሲስተር እማዋይሽና ለጀግናው አጴ ቴዎድሮስ መታሰቢያ ቤተ መዘክር ለማቆም ደፋ ቀና የሚሉት የአስተባባሪ ኮሚቴ አባላት ባደረጉት ጥረት አንድ እርምጃ የሄዱበት ወቅትም ነበር ፣ ለቴዎድሮስ መታሰቢያ ቤተ መዘክር መስሪያ መሬቱ ተሰጥቷቸው የመሰረት ድንጋይ ተጥሏል ፣ ከተደረገልኝ ገለጻ አልፎ ተርፎ በቦታው በመገኘት የመሰረት ድንጋዩ ያረፈበትን ቦታ ተመልክቻለሁ … በዚሁ አጋጣሚ ሲስተር እማዋይሽ ገሪማን ጎንደሬው አንስቶ ስለማይጠግባቸው ባለቤታቸው ዶር በርናንር ደጋግሜ ጠየቅኳቸው ፣ እማዋ ግን ስለራሳቸውም ሆነ ስለባለቤታቸው ብዙም አይናገሩም ። ሁኔታው ተመቻችቶ እግሬን ጎንደር ላይ ሳሳርፍ ብዙ ስለሚባልለት ጠቢብ ጥቂት ያወሩኝ ዘንድ መወትወቴ ገፋሁበት ፣ ከሲስተር እማዋ ጋር በአንዱ ቀን አብረን ታሪካዊዋን ከተማ ስንዘዋወር ላላሰለሰው ውትወታየ ጀሮ የሰጡት እማዋ በቁልምጥ ስሜን ጠርተው እንዲህ አሉኝ ” ነብያለም ስለዚህን ቅን ፣ ደግና ቸር ባለቤቴን ማንነት እኔ እንዲህ ነው አልልህም ፣ ደግሞም ስጋየ ነውና እኔ ብናገረው አያምርም ፣ ከምን ም በላይ ግን የሃገሬን አፈር ፣ ባህልና ወጉን እንዲያውቅ አድርጌዋለሁ ፣ ዛሬ ከእኔና ከአንተ በላይ ስለምትወዳት እናት ኢትዮጵያ የሚመሰክር የታሪክ ሊቅ ባይባል ተመራማሪ በመሆኑ ደስታየ ወሰን የለወም ፣ እኔ ለኢትዮጵያ ያደረግኩት ስጦታ በርናርድ ይመስለኛል ፣ የሚገርምህ እኔም ሆንኩ እሱ የምንሰራው ለነፍሳችን ነውና ማንም ይህንን ተመልክቶ እንዲያመሰግነን አንፈልግም ፣ በርናርድም የሚልህ ይህንኑ ነው ፣ አትቸኩል ፣ ሰውየውን ታገኘውና ታወጋላችሁ ” ነበር ያሉኝ ፈገግ እያሉ …

ብዙም ሳይቆይ ከቀናት በኋላ ከሲስተር እማዋይሽ ጋር ተገናኘን ፣ በተያዘልኝ ጠሮ መሰረት ከጎንደር ከተማ ወጣ ብሎ በሚገኘውና አባ ሳሙኤል ተብሎ በሚታወቀው መናፈሻና የከብት ማድለቢያ መንደር ስናመራ ቀዝቃዛ ንጹህ ነፋሻማ የቸቸላንና የሳሙና በርን አየር እየማግን ነበር ። … ከጎንደር ወደ አየር ማረፊ አቅጣጫ ፣ የአዘዞ መዳረሻ ሳሙና በር ድሮ ጥቅጥቅ ያለ ጫካ ነበር። በዚሁ ትላልቅ የጽድ ዛፎች በሚበዙበት አንድ ጫፍ ጀርባውን ለአንድ ቋጥኝ ሰጥቶ የተገጠገጠ ቤተ መንግስት የሚመስል ቪላ ተገንብቷል። ሲስተር እማዋይሽ መኪናቸውን እንደማብረድ እያደረጉ ወደ ቪላው ሲጠጉ ከውጭ በኩል እያመላከቱ ” አየህው በርናርድ ሃኪም ፣ ታሪክ ተመራማሪ ብቻ አይደለም ፣ ይህንን ቪላ ውስጡን በአስገራሚ የጥንታዊ ኢትዮጵያ ቁሳቁስ አሟልቶ የሰራ ” አርክቴክት ነው ! ” ሲሉ በፈገግታ ጠቁመውኝ ወደ ግቢው ገባን …


ከመኪና ወርደን ወደ እንግዳ መቀበያ አዳ ራሹ ስናመራ በግቢው አጥር ስር የተተከሉ አትክልቶችን ውሃ የሚያጠጣ እድሜው መጠ ጥ ያለ ጸጉረ ልውጥ ሰው ተመለከትኩ ። በአ ግራሞት ስቁለጨለጭ ሲስተር እማዋ በሁኔታ ፈገግ አሉና “ሰውየው ይህውልህ ” አይነት ምልክት በፊታቸው እየተነበበ ሰውየውን አስተዋወቁኝ። ሰውየው ዶር በርናርድ ነበሩ …

ዶር በርናርድ በፍልቅልቅ ፈገግታቸው ተቀብለው ሲኮተኮቱ ነበርና አፈር የነካ እጃቸውን እስኪተጣጠቡ ለሲስተር እማዋይሽ አስረከቡኝ ፣ እማዋይሽም በተንጣለለው የእንግዳ መቀበያ አስገቡኝ ። እግሬን ከግቢው ሳስገባ ጀምሮ ኢትዮጵያዊነትን የሚገለጽባቸው በሚያምር ሸክላ በእውቀት የተሰሩ የአበባ ማስቀመጫ እንስራዎች ፣ ድስቶችና ከመሳሰሉት አልፎ ተርፎ አዳራሹ በደረጃው ከፍ ባለ ቅርሳ ቅርስ ፣ ብሔር ብሔረሰቦችን አጉልቶ የሚያሳየው ቁሳቁስ ያጌጠው ቤት ቀልቤን ሳበው ። የቆመው ልቤ መቀመጥን አልወደደውም ፣ ዙሪያውን ማየት ፈልጓል ! ደግነቱ ብዙም ሳይቆይ ዶር በርናርድ ” ይቅርታ ዘገየሁ አይደል? ” ብለው ከተፍ አሉ! ልነሳ የተቁነጠነጥኩት ጎረምሳ ከሃኪሙ ፣ ከታሪክ ተመራማሪው እና ከስነ ህንጻው ባለሙያ ጋር መቀመጥና አፍ ላፍ ግጥሞ ማውራት አማረኝ … ወጋችን ቀጠልን ፣ ዶር በርናርድንና የእህታቸውን ወንድም ፕሮፎሰር ሃይሌ ገሪማ አንድ ሳይሆን በርካታ የሚያመሳስላቸው ነገር እንዳለ ታዘብኩ … ዶር በርናርድ እንደ ፕሮፎሰር ሃይሌ ገሪማ የሚናገሩት ደረቅ እውነት ጥልቅ ነው ፣ የእኔ ትውልድም ሆነ ያ ትውልፍ ስለሚጎድለውና መሆን ስላለበት የሰላ ሂስ ከነ መፍትሔው ፣ ስለ ኢትዮጵያዊነት ባህል ፣ ስለ ታሪክ አሻራውና ስለይትበሃሉ የቅብብሎሽ ጉድለት ጥልቅ ምክክር ሳይሆን ምክርን ሰጡኝ ! ብዙውን ተደምሜ ግራ ቢገባኝ እርስዎ ዜግነትዎ ከወዴት ነው ? አልኳቸው ፣ ሳቁና አላፊ አግዳሚው ግራ እየተጋባ ስለሚጠይቃቸው መሰል ጥያቄ ሲመልሱ ” እኔ 400 አመት በፊት በአሜሪካና በጃማይካ ከምወዳት ሃገሬ ተለያይቸ የቆየሁ ኢትዮጵያዊ ነኝ ! ” በማለት መለሱልኝ ፣ በርናርድ ስለኢትዮጵያ ቀዳማዊ ታሪክ ፣ በባሪያው ንግድ ዘመን ስለተሰደዱት አፍሪካውያን ታሪክ በአስገራሚ ሁኔታ ተንትነው አስረዱኝ … ዝም ጭጭ ነበር ያልኩት … በህዎታቸው ዙሪያ ሰፊ ግንዛቤ የሰጡኝም በዚህ ወቅት ነበር ! እናም ካጫወቱኝና ከተሰራጨው የህይዎት ታሪክ መካከል የበርናርድን የአፍሪካና የኢትዮጵያ ትስስር እነሆ …

ዶር በርናርድ አፍሪካና ኢትዮጵያ …

ከሁሉ አስቀድሞ አንድ ለዚህ ዝክር ቅኝቴ ምንጭ የሆነኝ መረጃ ያገኘሁት የዶር በርናርድ ሬሳ በምድረ አሜሪካ የመጨረሻ ሽኝት የቀረበው የህይዎት ታሪካቸው መሆኑን መሆኑን ልብ በሉልኝ ፣ ከዚሁ መረጃ ጋር ዶር በርናርድን በአካል አግኝቸ ካጫዎቱኝን የመረጃ ግብአት እያዋሃድኩ ለአንባቢያን በሚመች መልኩ እንደሚከተለው አቅርቤዋለሁ ።

የጠቢቡ ሀኪም የህይወት ተልዕኮና የውስጥ ነፍስ ፍላጎት የሚጀምረው ከጃማይካውያን ብርቱ የኢትዮጵያ ወዳጆች ነው ። ከእነ ማርከስ ጋርቬ … በርናርድ ማርከስ ጋርቬ‘ ወደ የስፋዋ የራሳችን መሬት እንመለስ’ ወዳሉባት ጥንታዊ ት ቅድስት የኢትዮጵያ ምድር ሄዶ የማገልገል ፍላጎት በአሜሪካው የተደላደለ ህይዎት ቢወጠንም ምክንያት በባርነት ዘመን የተሰደ ድን የዚያች ሃገር ዜጎች ነን የሚል ብርቱ ምክንያት ነበረው ። ያ ህልሙና ራዕዩን እንዲሳካ ደግሞ የኑሮ አጋሩ የአርበኛው ደራሲ የገሪማ ታፈረ የአብራክ ክፋይ ሀገር ወዳዷ ሲስተር እምዋይሽ ምክንያት ሆነች። እናም ወደ ኢትዮጵያ ለመጓዝ ከምድረ አሜሪካ የተጸነ ሰው ቅዱስ ሃሳብ አፍሪካን በመጎብኘት አሃዱ ብሎ ተጀመረ … !

ዶር በርናርድ ታንዛኒያን እና ኬንያን ቀዳሚ ጉብኝት ሲያደርግ በአይኑ በብሌሉ የተመለከ ተው ፣ በአካል ያዳመጠውና የዳሰሰው የአፍሪ ካ ልጆች ገና ያልተቀረፈ ችጋር ነፍሱን አደማት ፣ የቀደምቷ “የዳቦ ቅርጫት “የአህጉረ አፍሪካን የኋልዮሽ ጉዞ ታዝቧልና ነፍሱን አስጨነቃት … አፍሪቃ የምትቃትትበትን የሰቆቃ መንገድ ፣ ጫንቃዋን የያዛትን የትላንቱ የቅኝ አገዛዝ ዛር እንዳልለቀቃት አይቶ አዘነ ፣ ተከዘ ! አጭሩን የታንዛንያ እና የኬንያ ጉብኝት አጠናቆ የሃገሩ ልጆች ጃማይካዎች “የተስፋዋ ምድር !” ብለው ወደሚያምኑባት ኢትዮጵያ አቀና …

ዶር በርናንድ ቅድስት ኢትዮጵያ …

የሚሰገመገመው አውሮፕላን የኢትዮጵያን ምድር ነካ ፣ የተቆለፈው የአውሮ ፕላን በር ተከፈተ ፣ በርናርድ እና ነፋሻው ውብ የተፈጥሮ ጣዕም ያለው የተስፋዋ ምድር መዲና የአዱ ገነት ቀዝቃዛ ንጹህ አየር ተገናኙ ፣ አየሩን ሲምገው – ህልሙን አስታወሰው ! … እንዲያ እያለ ጉብኝቱን ጀመረ ! ዶር በርናርድ ሀኪም ነውና በሚያውቀው ሙያ ዳሰሳ ለማድረግ ይመቸው ዘንድ በኢትዮጵያ የመጀመሪያ ቀናት ቆይታው የህክምና ተቋማቱን ጎበኘ ። በየህክምና ተቋማቱ ሕሙማኑ ተኮልኩለው እርዳታ ለማግኘት ሲጠባበቁ ቢመለከት ልቡ ተሰበረ። አዲስ አበባ ጥቁር አንበሳ ሆስፒታልና የህክምና መካነ ጥናት እንዲሁም ቅዱስ ገብርኤል የግል ሆስፒታል ሲጎበኝ፤ ረዠም ራዕዩን ፣ የህክምና ልሂቅ የመ ሆን ዝናውን ያወቁበት ህልሙን የነቁበት ” የእኛ ሁንልን ” ሲሉ ተማጸኑት ! በንዋየ ፍቅር ደንታ ለሌለው ፣ ለሰብዕና ቅድሚያ ለሚሰጠ ው ለዶር በርናርድ ይህ ግብዣ ተቀባይ አልነበረውም ፣ አልተቀበለውም ! የጠቢቡ ጉብኝት ቀጥሏል …

አኩሪ ታሪክ ባህሏን ጠንቅቆ እንዲረዳ ፣ እንዲማርና እንዲመራመር ፣ በኢትዮጵያ እና በኢትዮጵያውያን ፍቅር እንዲነደፍ ፈር በቀደደ ችው የትዳር አጋሩ በሲስተር እማዋ ገሪማ እየተመራ ኢትዮጵያ አሳምሮ ጎበኛት ። ጠቢቡ ከሰማ ካነበበው የኢትዮጵያ ታሪክና ባህል በላይ ያጣ የነጣው አብዛኛው ህዝብ ሰው አክባሪና እንግዳ ተቀባይነትና ታማኝነት በኩራት ሲያስደምመው ። የድህነቱና የችግሩን መክፋት ግን ህመም ሆኖ አስከፋው ! ዶር በርናርድ አንደርሰን ድህነት ፣ በሽታው መገፋት የሚችል እንደሆነ ከማውጠንጠን መፍትሄ ፈልጎ በእሱ መደገፍ የሚችለውን ድርሻ አውጥቶ መተግበር ጀመረ እንጅ ድህነት ፣ ችግሩ አንገሽግሾት ወደ መጣበት ሽሽትን አልመረጠም ! ከተሜውን ጎብኝቶ ወደ ገጠሮቹ ሊመለከት አዘገመ። የሀኪም እጅ ማየት አይደለም መልኩና ገጹ የናፈቃቸውን ወገኖች አጋጠሙት። በርካታ ኪሎ ሜትሮችን አቋርጠው መጥተው ከየሆስፒታሉ ደጃፍ ተኮልኩለው አምላካቸውን እየተማጸኑ፤ ከእለታት አንድ ቀን የሀኪም እጅ እንዲነካቸው ሳምንታትን የሚጠብቁ ምስኪኖች ልቡን አሳዘኑት ፣ መንፈሱን ነኩት …

ጎንደርም በፍቅሯ ነደፈችው ፣ እንግዳዋን በፍቅር ተቀብላ ” የእኔ ሁን ፣ ቅርልኝ! ” አለች ው ። ዶር በርናርድ የእናት ጎንደር ጥሪዋን በጸጋ ተቀበለ ! ከግማሽ ምዕተ አመት በላይ እድሜን ላስቆጠረው ብቸኛው የጎንደር ሆስፒ ታልን ለማገልገል ለህክምና ኮሌጁ የአሁን ብሩህ ተስፋ እጁን ሰጠ። ከህክምና ድጋፉ ፣ በተጓዳኝ ጥናትና ምርምሩ አንቱ በሚያሰኘ ውን ተመክሮ ራሱን እያጎለበተ ጉዞ የጀመረው ሃኪም ህክምና ድጋፍ ከመስጠት ርቆ ሔዶ በመምህርነት ሙያው ተተኪ ትውልድን የማነጽ ህልሙን ከሞላ ጎደል አሳካ ! በጎ ስራውን የዋሽንግተን ዲሲ በርካታ ኢትዮጵያ ውያንን ጨምሮ የጎንደር ተወላጆች የዶ/ር በርናርድ አንደርሰን ቅን በጎ አድራጎት በመረ ዳት ስህክምናው በሰፊው እጆቻቸው አቀፉት። ዶር በርናርድ ፋታና እረፍት አላስፈለገውም።

ቀድሞውንም እረፍትና ምቾቱ ለህሙማን መድረስ – ለተቸገረ ዋስ መሆን ነበርና ደከመኝ ሰለቸኝ ለዶ/ር በርናርድ ዋጋ አልነበራቸውም። ከአጸደ ስጋ እስከተለየበት ጊዜ ድረስ የስራና ሰውን የማገልገል ቀናት ናቸውና። ከሁሉም የሚያስገርመው ደግሞ “እስመ ትህትና ረከበ ልዕልና” እንዲባል የህክምናው ሊቅ እኔን እዩኝ ሳይል – አለሁ ብሎ ሳይፎክር – እወቁኝ ብሎ ሳያውጅ – ካልተለወደበት ወገን መካከል ከእግር ስር ሆኖ አገለገለ። እንደ ሀገሬው ቋንቋውንና ባህሉን አጥንቶ ፣ እጅ ነስቶ – በባላገሩ ምርቃት ተመርቆ ትሁት እንደሆነ ኖረ። የአሜሪካ ኑሮና ገንዘቡ ሳያሳሳው ይልቁንም ለዘመናት ለፍቶ ያፈራውን – ሰርቶ ያቆመውን ይዞ – ጎንደር ከሆስፒታል ደጃፍ ለሚጠኑት ዋለላቸው ፣ በፍቱን እጁ ዳሰሳቸ ው ፣ ለወሮታው አመሰገኑት !

ከየህክምናው ተቋም ተኮልኩለው የሚያያ ቸው ህሙማን ቢያሳዝኑት – መጠለያ ለማሰራ ት ወጠነ። ሀገር አቆራርጠው ለህክምና የሚ መጡን ለመታደግም ሆስፒታል አስገነባ። በአዘዞ በዶ/ር በርናርድና በባለቤቱ የተገነባው ይህ ሆስፒታልም ለመቶ ህሙማን ማርፊያ መኝታ እንዲኖረው ተደርጎ ተገነባ ፣ ምንም እንኳን ሆስፒታሉን ስራ ጀምሮ ለማየት ዶ/ር በርናርድ በስጋ ቢለይም እንደሙሴ የቃል ኪዳን ሀገር – ስሙን የተከለበትን ራዕይ ለእኛ ትቶልን በክብር ተሸኝቷል !

ዶር በርናርድ አንደርሰን የህክምና ሊቅ ብቻ አልነበረም። ዘርፈ ብዙ ተሰጥኦም ነበረው። በስነ ህክምናው በጣፊያና በጉበት ህመም ለሚሰቃዩ በልዩ ጥበብ ብልቶቹ የሚሰሩበትን ዘዴ በምስል ነድፎ የባለቤትነት (ፓተንት) ያለው ባለሙያ ነበር። ዛሬ መዝገብ የያዛቸው በዓለም አቀፍ ደረጃ የባለቤትነት ዕውቅና የያዘባቸው ሁለት መሳሪያዎች አሉት። በታሪክ እውቀቱና አስተምህሮ የአፍሪቃን አስተሳሰብ የተከተለ – እውነተኛን ስር ፈልፍሎ በማውጣት በምስል – በጥናታዊ ጽሁፍ ያቀናጀ ፤ በህንጻና በቤት ውስጥ ማስዋብ ጥበብ የተካነ ( ሆስፒ ታሉም – የዶ/ር አንደርሰን ዲዛይን በዶር በርና ርድ የተሰራ ነው) በስነ ግጥም መጽሀፍ የጻፈም ብዕረኛ ነበር። የስነ ግጥሙ ስብስብ መጽሀፍ ርዕስ Limbic glimpses ይሰኛል።
ዶር አንደርሰን ኢትዮጵያን አውቋት ነው የወደዳት። እኛ አልታይ ያለንን ውበቷን አየው ፣ ፣አኛ አልታይ ያለንን ፣ አለያም አይተን መፍትሔ ያጣንለትን የወገን ችግር ተረድቶ በተግባር ችግሩን ለመቅረፍ የተጋ ሰው የኢትዮጵያ ወዳጅ ነበር ። እኛ ጥለን በምንሸሻትን ሃገር ፣ እኛ የምንለያይበትን ታሪክ አንጠርጥሮ ተረድቶታል ፣ በፍቅሯን እርሱ ሁሉን ተሸከመው። እኛ ጥለናት የሸ ሸናትን እሱ በህይወት በሞትም እንደፈለጋት “ልሁንልሽ፣ በቀሪ ህይዎቴ አገልግልሻለሁ! ” እንዳላት ብቻ አላለፈም ከዚህ ሁሉ ባላይ መንፈሳዊ ህይወቱንም ከጥንታዊው እምነቷ ጋር አዋህዶ – በህልፈተ ህይወቱም አፈሯን ሊለብስ ጸሎተ ፍታት እንዲደረግለት ከእርሷ ማህጸን ሊመለስ ተናዘዘም። እንዳለው ይሆንለት ዘንድ ውድ ባለቤቱ ወዳጆቹና አፍቃሪዎቹ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ እምነት ተጠምቆ – ፍታቱንም በመንፈሳዊ ስርዓት እንዲሆንለት እንተደመኘ ሆነለት !

ከዶ/ር በርናርድ የህክምና ጥበብን ብቻ ሳይሆን ርህራሄን – ሌሎችን የማገልገል መርሀ ጽድቅን – ራስን ከመውደድ የመውጣት ትልቅነትን ተማርን። ደከመኝ ሰለቸኝ ሳይሉ – ምንምን ሳይንቁ ሰው የመሆንና የመባልንም እውቀት ቀሰምን። ዶ/ር በርናንድ ተናግሮና አውርቶት ሳይሆን ኖሮት አሳየን። በዚህች ቅጽበት መለስ ብለው ሲያስቡት ዶ/ር በርናርድ እኛ ቀረብን – አመለጠን እንጂ እሱማ ክቡር የህይወት ተልዕኮውን አጠናቋል። ሩጫው ለእኛ አጠረብን እንጂ እሱማ ህልሙንና ራዕዩን አከናውኗል። የማገልገልን የቃል ኪዳኑን ምድር አሳይቶናል። ክቡር ሞቱ ለሰማዕቱ ይባልለታል። ዶ/ር በርናርድ ኖሮና ሰርቶ – እኛ ያለወቅናትን ኢትዮጵያ አውቋትና አሳውቆን – የመሆንና የማድረግን ምስጢር አስቃኝቶን ነው ከአጸደ ስጋ የተለየው። ህይወት የእግዚአብሔር ስጦታ ናትና ለአፍታም ቢሆን ዶ/ር በርናርድን ያህል ሰው ሰጥቶና አሳይቶን ወሰደብን።

የህክምና ጠቢቡ ለራሱ አልሆን ብሎ በውስጥ ደዌ ተቀስፏልና በአሜሪካን ዋሽንግተን ለወራት በህክምና ሲረዳ ቢቆይም የተቆረጠችው ቀን ደረሰች ፣ ዶ/ር በርናንድ እድሜውን ድሆችን በመደገፍ ፣ አቅመ ደካሞችን በመንከባከብ ፣ በውስጥ ደዌ የተጎዱትን አክሞ በመፈዎስ የተጋው ዶ/ር በርናንድ አንደርሰን ላንዴና ለመጨረሻ ጊዜ አሸለበ ! ዶ/ር በርናርድ የሁለት ወንድ ልጆች አባት ነበር። ታህሳስ 24 ቀን 2007 ዓም ወይም እጎአ ጥር 2 ቀን 2015 ዓም በህክምና ለጥቂት ወራት ሲረዳ ቆይቶ ከዚህ አለም በሞት ተለየን … !

ዶር በርናርድ ብራድሊ አንደርሰን “በቀሪ ህይዎቴ ኢትዮጵያን አገለግላለሁ ” ብሎ ቃሉን ፈጽሞ የጉዞው ፍጻሜ ሲቃረብ የሬሳው የመጨረሻ ማረፊያ የተወለደባት ጃማይካ አለያም የተማረ ያደገ ፣ የተሸለመና ዜግነት ሰጥታ ባኖረችው ሀገረ አሜሪካ እንዲያርፍ አላደረገም ። ከጎንደር ታሪካዊ ቦታዎች አንዷ በሆነችው በታሪካዊዋ ቁስቋም ማርያም ደብር እንጅ … ጥር 2 ቀን 2007 ዓም የዶር በርናርድ ብራድሊ አንደርሰን የቀብር ሥነ ሥርዓት ወዳጅ ዘመድ ፣ ተማሪ ዎቹ ፣ የስራ ባልደረቦቹና ሀገሬውና አድናቂዎቹ በነቂስ በመገኘት “ስምህ ህያው! ” ነው ሲሉ በእንባ ተራጭተው በክብር አፈር አልብሰው የመጨ ረሻው ሽኝት በሃዘን በተሰበረ ልብ ተከው ኗል…እነሆ ኑዛዜ ቃሉም ተፈጸመ ! ጠቢቡ ጃማይካዊ ዶር በርናንድ መቀበሪያውን ኢትየጵያ / ጎንደር ውስጥ በአንድ ኮረብታ ማማ ላይ በምትገኘው በታሪካዊዋ የቁስቋም ማርያም ደብር ሆነ !

የዶር በርናርድ ብራድሊ አንደርሰን ! ክብርና ሞገስ ይገባሃል ! እንዎድሃለን እናከብርሃለን !

Dr. Bernard Bradley Anderson we are very proud of you & Thank you !

ነፍስ ይማር !

ነቢዩ ሲራክ
ጥር 3 ቀን 2007 ዓም

በጀርመን ፍራንክፈርት ከተማ የተቋቋመው የሃገር ፍቅር የሥነ ጥበብ መድረክ ጥር 16 ቀን 2007 ያቀርባል

0
0

በጀርመን ፍራንክፈርት ከተማ የተቋቋመው የሃገር ፍቅር የሥነ ጥበብ  መድረክ ሁለተኛ ዝግጅቱን ጥር 16 ቀን 2007/ ጃንዋሪ 24 /2015 በፍራንክፈርት ከተማ ያቀርባል። ስለ ዝርዝሩ የተያያዘውን ማስታወቂያ ያንብቡ ።

ty

ገዢ ቢሰባ ለመሬት አህያ ቢሰባ ላራዊት

0
0

ቢኒያም ግዛው ከኖርዌይ ኦስሎ

ይሄ ምርጫ መቼስ ስንቱን ያስታውሰናል?በደርግ ዘመን እናቶች ወንድ ልጃቸውን ከየጉያቸው እየተነጥቁ እና እየታፈሱ በጦርነት ሲማገዱ ወንድ ልጅ ላለመውለድ. . . ትዝም አላለሽ ወይ የክፉ አመቱ ላንቺና ለልጅሽ ያለቀ ስንበቱ ማህጸኔን ዝጋ ይቅር ምን አባቱ በእንባ እየዳከርሽ ብለሽ ያልሽበቱ። እያሉ ፈጣሪን ወንድ ልጅ እንዳይሰጣቸው የለመኑትን ቤቱ ይቁጠራቸው። የአፈሳና የሀገራችንን አንድምታ ለመረዳት ከሰሞኑ በየከተማዎችና ጎዳናዎች ያለው የድብደባ የአፈሳና የሞት ፍርሀት ድባብ ተቀባብሎ ለቃታ የተዘጋጁ ጥይት በእያንዳንዱ ሰላማዊ ዜጋ ጆሮ ስር ተደግኖ እንደሚራመድ በቀላሉ መረዳት ይቻላል።
. . . ጭቃ ከማቡካት ጀምሮ አብሬው ያደኩት ጓደኛዬ ስሙ ጌታቸው ይባላል። እንዴት እንደምንዋደድ እንደምንተሳሰብ እና እንደምንመካከር አትጠይቁኝ። በቃ ጌቾ ምርጥ ጓደኛዬ ነው።
እናም በጊዜው ወያኔ መዲናችን አዲስ አበባ ገቡ ገቡ የሚባልበት ሰአት ኖሮ ግራ መጋባቴን ከባልንጀራዬ ላወራ በአጥር በኩል ጌቾ!ጌቾ! ብል እናቱ ወ/ሮ በለጥሻቸው ከየት እንደመጣ የማይታወቅ ከበሮአቸውን ጸሀይ ላይ እያገላበጡ ግቻ ያርግህ. . . ጎይቶም አትልም! ብለው ቀልቤን ገፈፉት። ነገሩ ወዲህ ኖሮ እሳቸውም ወ/ሮ በለጥሻቸው ታጋይ ትብለጽ ተብሎ ስማቸው መተርጎሙን ያወኩት ቆይቼ ነገር ከገባኝ በኋላ ነው። ከዚያማ እነአቶ ክፍሉ (ክፍለእግዚእ) እነአዲስ (ታጋይ ሀዲሽ) ወዘተ ስናዳምጥ የጫካ ስም ብቻ ሳይሆን የከተማም ስም እንደነበራቸው ተረዳን።
ከዛ በኋላማ ምኑን ልንገራችሁ በኳስ ሜዳ ሰው የጠፋ ጊዜ በረኛ ካልሆነ ወደ ውጪ የወጣ ኳስ አቀባይ የነበረው ጊቾ በግልጥ ፎሪ የወጣውን እንደፈለገ እና ደስ እንዳሰኘው ጎል ብሎ ሲያፀድቀው ቢደብረንም መስማማት ብቻ ሆነ። አይ የቀን ክፉ! ግንቦት 20። ይኽው እስክንበታተን ድረስ ጎይቶምም እንደኛ ባሉት ላይ ተቀይሮ ሲጎለብት ታጋይ ትብለፅ ደግሞ እነማዘርን በዳቦ ተቆጣጥረው ሲጠረንፉን ከረሙ።
ጦጣ በአንድ ወቅት ለቃለ መጠይቅ ቀርባ ኖሮ ምን ትወጃለሽ? ተብላ ብትጠየቅ የዛፍ ላይ ትግል አለች አሉ። በፀዳ ሜዳ ግልፅነትና እውነት ባለበት ምርጫ እንደ ኢትዮጵያ ባሉ ሀገሮች ማየት ከንቱ እየሆነ መምጣቱ በዕጅጉ ያሳዝነናል ። አንድ ጎጠኛ ብሔረሰብ ብቻ በሚመቸው ፓርላማና በየቀበሌው እንደ ጦጣ በስልጣኑ ላይ እየተንጠላጠለ 23 ዓመት መግዛቱ ስርዓቱ ምንኛ አስከፊ መሆኑን የሚያሳይ ነው።
ኢትዮጵያ ለዘመናት ተከብራ የኖረችና ህዝቦቾም ልዩነትን ወደሆላ በመተው በጋራ ፣በመቻቻል ፣በመካባበር ሀገራቸውን አስከብረው ከዘር እና ከእምነት ይልቅ ኢትዮጵያውነትን በማስቀደም ኢትዮጵያዊነት የገነነባት ሀገር እንደነበረች ይታወቃል እነሆ ዛሬ ወያኔ የሁትሱና ቱትሲን ስርዓት ናፍቆ ገዢ ከኔ ዘር ሌላ ለአሳር እያለ ሰፊውን ህዝብ ለጦርነት ጋብዞታል። ወያኔ ፈጽሞ በኢትዮጵያዊነት የማያምን እና የኢትዮጵያ ህዝበም በአንድነትና በፍቅር እንዲኖር የማይፈልግ ጸረ ኢትዮጵያዊ ሲሆን ይህንንም በመረዳት እኛ ኢትዮጵያኖች አንድነታችን ለወያኔ የራስ ምታት መሆኑን አውቅን  አንድነታችንን የሚያጠናክር ስራዎች ላይ ልናተኩር ይገባል :. ዘረኛው የህህዋት መንግስት በአንድ ወቅት አርሱ አደሩ የሀገሬን ገበሬ እኔ አውቅልሀለሁ እያለ ካለበት ሀገር መሬትና ቀኤ ድረስ መጥቶ ልግዛህ እያለ መከራውን ሲያበላው . . .
ሳለቅስ ሳነባ የሰጠኽኝ ሸማ ጉድ በል ያገሬ ልጅ እንካ መርዶ ስማ የወንዝህ ማዕረግ በትግሬ ተቀማ
እያለ ለአያትና አባቱ በቅኔ ብሶቱን መናገሩ አፈናና ረግጣውን ቅሚያና ዘረፋውን መቋቋም ቢያቅተው መሆኑ ልብ ይሏል። የፈረንሳዩ ደራሲና ፈላስፋ ቪክቶር ሁጎ “When dictatorship is a fact, revolution becomes a right.” ብሎ ማለቱ አንደ ወያኔ ላለ በአንድ ብሔር የበላይነት ተንፈናጥጦ እንደፈለኩ ልግዛህ ለሚል መንግስት ትክክለኛ አባባል ነው።
ምርጫ ፍትህና ዴሞክራሲ ምን እንደሆነ ለማይገባው መብት ማስከበሪያው ብቸኛ መንገድ ለለውጥ ፀንቶ መታገል ብቻ ነው። በአሳማ መንጋ የምርጫ ውድድር ያው አሸናፊው አሳማ እንጂ ነብር ወይ አንበሳ አይሆንም። በመሆኑም ያው አሳማ ነገም ልርገጣችሁ ማለቱ አይቀርም። በሰብዓዊ ትግል ተስፋ አይቆረጥም የሰፊው ህዝብ መብት ታላቅ ውቅያኖስ ነውና ጥቂት የአምባገነን ጠብታ ሰፊውን ባህር አያደፈርሰውምና አሁንም የሰብዓዊ መብት ትግል አሸናፊ ነው። በጥቂት ዘረኞችና በአንድ ጎሳ የበላይነት የተያዘው የወያኔ አገዛዝ የሰፊውና የታላቁን የኢትዮጵያ ህዝብ ትግል በምንም መልኩ ሊገታው አይገባም ይልቁንም ”ገዢ ቢሰባ ለመሬት አህያ ቢሰባ ላራዊት” እንዲሉ በማን አለብኝነት የተንሰራፋውን ወያኔና አግዛዙ መቃብሩ ተምሶ ያለቀ መሆኑ ግልፅ ነው። እናም በሁሉም አቅጣጫ የትግላችንን ትንቅንቅ ልንቀጥል ይገባል እላለሁ።
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ !!!
Comment

ትብብሩ ምርጫ ቦርድ የመድብለ ፓርቲ ስርዓትን በር ለመዝጋት እየተጋ መሆኑን አስታወቀ

0
0

• ‹‹ምርጫ ቦርድ ለገዥው ፓርቲ በአጥቂነት ቦታ ተሰልፎ እየተጫወተ ነው››

e1022b6eየ9ኙ የተቃዋሚ ፓርቲዎች ትብብር ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ የመድብለ ፓርቲ ስርዓትን በር ለመዝጋት እየተንቀሳቀሰ ነው ሲል ቅሬታውን ገለጸ፡፡ ትብብሩ ጥር 4 ቀን 2007 ዓ.ም በሰማያዊ ፓርቲ ጽ/ቤት በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ እንዳስታወቀው ምርጫ ቦርድ ከህግ አግባብ ውጭ በሆነ መልኩ የፓርቲዎችን ትብብር ‹ህገ-ወጥ› በማለትና በአባል ፓርቲዎቹ መካከል ‹አሰባሳቢና ተሰባሳቢ› እንዳለ በማስመሰል አለመተማመን ለመፍጠር የሚያደርገው እንቅስቃሴ ተቀባይነት የሌለው ነው ብሏል፡፡


ትብብሩ የትብብሩ አባል ፓርቲ የሆነው ሰማያዊ ፓርቲ ከምርጫ ቦርድ ‹‹ትብብር በሚል ማሰባሰብን›› እንደ ጥፋት ቆጥሮ ይቅርታ እንዲጠይቅ ደብዳቤ መጻፉ ተገቢነት የሌለውና ትብብሩ የሚያወግዘው መሆኑን አስታውቋል፡፡


ቦርዱ በአደባባይ ‹‹ፓርቲዎችን በእኩል ዓይን ነው የምመለከተው፣ በሆደ ሰፊነት እያስተናገድኩ ነው›› ቢልም፣ በፓርቲዎች መካከል አድሎ እንደሚፈጽም በማስረጃ ማስረዳት እንደሚችል የገለጸው ትብብሩ፣ የሚከተሉትን ነጥቦች በዋቢነት አንስቷል፡፡


1. ገዥው ፓርቲ/መንግስት ‹‹ነጻነት ለፍትሓዊ ምርጫ›› በሚለው ፕሮግራማችን ህገ-መንግስታዊ መብታችን ተጠቅመን የጠራናቸው የአደባባይ ስብሰባዎችና ሰልፍ በማፈን ህገ-ወጥ እርምጃ ሲወስድ ቦርዱ ‹‹ህገ ወጥና እኔ የማላውቀው ትብብር ነው›› በሚል ክስ ማቅረቡ፣


2. ለሰማያዊ ፓርቲ በጻፈው ደብዳቤ የትብብሩን አባል ፓርቲዎች በማበላለጥ አሰባሳቢና ተሰብሳቢ፣ የሁከት ጠንሳሽና ጀሌ፣ በማለት ያለ መተማመን ስሜት በመፍጠር ለመከፋፈል ያደረገው ሙከራን መጥቀስ ይቻላል ብሏል በመግለጫው፡፡


ፓርቲዎች በትብብር የጋራ አቋም ለመውሰድም ሆነ የጋራ ተግባር ለመፈፀም የቦርዱ እውቅና እንደማያስፈልግ፣ ከዚህ በፊት ለበርካታ ጊዜያት ፓርቲዎች በጋራ የጠሯቸውን ሰላማዊ ሰልፎች፣ በህጋዊ ሰውነታቸው የመሰረቷቸውን ግንኙነቶች (የኢተፓዴኀ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት፣ መኢአድ፣ ኦብኮ፣ ደቡብ ህብረት ኀብረትና አማራጭ የመሰረቱትን ‹ትዲኢ›› እና 33ቱ) አውቀው መርሳታቸው፣ ገዥው ፓርቲ አምስት ክልሎችን ከሚመሩ ፓርቲዎች ጋር አጋር በሚል የሚያደርገው ግንኙነት ከእኛ ትብብር ቀርቶ በግንባር ከተደራጁ ያለፈና የጠነከረ መሆኑ የአደባባይ ምስጢር ሆኖ ለዘመናት በዘለቀበትና አንድም ቀን ጥያቄ ባላነሳበት፤ ቦርዱ በአዋጅ ባልተሰጠው ሥልጣን ለገዥው ፓርቲ ‹አጋር መልማይ› ወይንም የህወሓት/ኢህአዴግ ‹‹ገንዘብ አዳይ ሆኖ ለተለዩ ፓርቲዎች ዳረጎት በሚሰፍርበት እውነታ ውስጥ ሆኖ ትብብሩ ላይ ጣት መቀሰሩን በማሳያነት አንስቷል፡፡


በመሆኑም ‹‹ትብብራችን በገዥው ፓርቲ ላይ የፈጠረውን የፍርሃት ስሜት የትብብራችን የጋራ እንቅስቃሴም ለገዥው ፓርቲ ሥጋት መፍጠሩን ለዚህም ምርጫ ቦርድ ይህን አይነቱን ህገ-ወጥ ፖለቲካዊ ድጋፍ በመገናኛ ብዙሃን በማሰራጨት ህዝቡ የሚሰጠንን ሁለንተናዊ ድጋፍ ለመግታት ወይንም ፈሪ ከተገኘ ለማስፈራራትና ለማሸማቀቅ የሚደረግ ተራ ፕሮፖጋንዳ ነው›› ብሏል፡፡


በአጠቃላይ ቦርዱ እየፈጸማቸው ያሉትን ተግባራት በህገ-መንግስቱና የምርጫ ህጉንና ሌሎች የአገሪቱ ህጎች ከተጣለበት ከባድ የዳኝነት ኃላፊነት ወጥቶ ለገዥው ፓርቲ በአጥቂነት ቦታ ተሰልፎ የሚጫወት መሆኑንና ይህም በሕገ-መንግሥት የተቀመጠውን የመድብለ ፓርቲ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ሂደት ከደረሰበት ወደኋላ የሚመልስ አካሄድ ነው ሲል ገልጹዋል፡፡


በመጨረሻም ትብብሩ ህገ-መንግስቱን አክብሮ እስከተንቀሳቀሰ ድረስ በትብብር ከመስራትና የጋራ ህጋዊና ሰላማዊ ትግል ከማድረግ ለአፍታ እንደማያቆም አስታውቋል፡፡

ነገረ ኢትዮጵያ / Negere Ethiopia

ጋዜጠኛ ሲሳይ አጌና በግንቦት 7-አርበኞች ግንባር ውህደትና በኢሳት ጋዜጠኞች የአስመራ ጉዞ ዙሪያ ለህብር ራድዮ የሰጠው ቃለምልልስ

0
0

ጋዜጠኛ ሲሳይ አጌና ከላስቬጋስ ከሚሰራጨው ሕብር ራድዮ ጋር ባደረገው ቃለ ምልልስ ግንቦት 7 እና አርበኞች ግንባር ስላደረጉት ውህደት; እንዲሁም የኢሳት ጋዜጠኞች ወደ አስመራ መሄድ ዙሪያ ማብራሪያ ሰጥቷል:: ያምድጡት::

Download (TIFF, 444KB)

Hiber Radio: የሕወሓት አስተዳደር ተለጣፊ አንድነት ፓርቲ መመስረቱ…የግንቦትና አርበኞች ግንባር ውህደት መነቃነቅ መፍጠሩ…ባለስልጣናቱ ለውጭ ሚዲያዎች የዋጋ ግሽበት መኖሩን ማመናቸውና ሌሎችም

0
0
ጋዜጠኛ ሃብታሙ አሰፋ

ጋዜጠኛ ሃብታሙ አሰፋ

የህብር ሬዲዮ ጥር 3 ቀን 2007 ፕሮግራም

የኢሳት ኤርትራ መግባትና የአርበኞች ግንባርና የግንቦት ሰባትን ውህደት በተመለከተ ከጋዜጠኛ ሲሳይ አጌና ጋር ቆይታ አድርገናል (ሙሉውን ያዳምጡ)

<…ምርጫ ቦርድ በአራት ቀን ውስጥ ጊባዔ አድርጉ አለ ባልጠበቀው ሁኔታ ከመላው አገሪቱ ጉባዔተኛው መጥቶ ጉባዔው ሲደረግ በስፍራው ሳይገኝ ተለጣፊ አንድነት አቋቁሜያለሁ አለ ። ኢ/ር ግዛቸውን የመረጠው የጠቅላላ ጉባዔ አባላት መካከል ከ209 በላይ ተገኝቶ አቶ በላይ ፈቃዱን መርጧል ሕግ የለም እንጂ ሕግ ቢኖር ያ በቂ ነው ከዚህ በሁዋላ አንድነት ከሚበረከክ ቢፈርስ ይሻላል ….>

አቶ አስራት አብርሃም የአንድነት ተጠባባቂ የሕዝብ ግንኙነት የነበሩ የዛሬውን የአንድነት ጉባዔና የምርጫ ቦርድን ሕገ ወጥ አካሄድ በተመለከተ ከሰጡን ማብራሪያ(ሙሉውን ያዳምጡት)

በፓሪስ የተደረገው የሽብር ጥቃት፣ የመናገር ነጻነትና ተከትሎት የመጡት ጥአቄዎች(ልዩ ዘገባ)

<<የሞት ጉዞ>> መጽሐፍ ደራሲ ከሆነው ጋዜጠኛና ደራሲ ግሩም ተክለሀይማኖትን ካለበት የመን እንዲሁም የ <<ምስጦቹ>> መጽሐፍ ደራሲ ተዘራ ታምራትን ከግብጽ ካይሮ ስለ መጽሐፋቸው አወያይተናል (ሙሉውን ያዳምጡት)

ሌሎችም

ዜናዎቻችን

በኢትዮጵያ ያለው የዋጋ ግሽበት እየጨመረ መሔዱን የአገዛዙ ባለስልጣናት ለውጭ ሚዲያ አመኑ

በኢትዮጵያ የመጀመሪያ የሆነው ጥንታዊው ጣይቱ ሆቴል ዛሬ በተነሳው የእሳት ቃጠሎ ከፍተኛ ውድመት ደረሰበት

የኢትዮጵያ አየር መንገድ አውሮፕላን ጋና ላይ ተከስክሶ ወደቀ

አንድነት ፓርቲ በአስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤው ፕሬዝዳንቱን ደግሞ መረጠ

ምርጫ ቦርድና ሕውሓት በጋራ አንድነት የሚል ተለጣፊ ድርጅት ፈጥረው ፕሬዝዳንት ያሉት ተመረጠ

በተለጣፊው አንድነት ምርጫ ላይ አባላት ያልሆኑና የደህንነቱ መ/ቤት ሰዎች በአካባቢው እንደነበሩ ለማወቅ ተችሏል

ትንሳኤ ኢህአፓ በድርጅቱ ስም የሚንቀሳቀሱት ቡድኖች ከእርስ በእርስ ጥሎ ማለፍ ለፀረ ወያኔ ትግሉ ቅድሚያ በመስጠት ዛሬም አንድ ላይ እንዲመጡ ጠየቀ

የግንቦት ሰባትና የአርበኞች ግንባር ውህደት በአገር ውስጥና በውጭ መነቃቃት እየፈጠረ ነው

ሌሎችም ዜናዎች አሉ


UN Says South Sudan Rebels Killed 306 People in April Attack

0
0
By William Davison, Jan 9, 2015  South Sudanese rebels allied to former Vice President Riek Machar killed at least 306 civilians when they retook the capital of oil-rich Unity state on April 15, theUnited Nations mission in the country said. Insurgents murdered more than 287 people in a mosque in Bentiu, many of them traders […]

Alemneh Wassie Report on Taitu Hotel Fire (Must Listen)

0
0
Alemneh Wassie Report on Taitu Hotel Fire (Must Listen)

Fasil Demoz – Yawelachu (Must Listen New Song)

0
0
Fasil Demoz – Yawelachu (Must Listen New Song)

Hiber Radio Special Interview with Sisay Agena on a recent visit ESAT journalists to Eritrea

0
0
Hiber Radio Special Interview with Sisay Agena on a recent visit ESAT journalists to Eritrea

Andargachew Tsgie Before the T-TPLF Inquisition? By Alemayehu G. Mariam

0
0
By Alemayehu G. Mariam “Cirque d’Andargachew” presented by the Ringling T-TPLF Brothers Voltaire (François-Marie Arouet) is often credited with the observation that one should “judge a man by his questions rather than his answers.” Voltaire also wisely observed, “All murderers are punished unless they kill in large numbers and to the sound of trumpets.” How […]
Viewing all 15006 articles
Browse latest View live