Quantcast
Channel: Ethiopian News | ዘ-ሐበሻ | Latest News Provider | News For All
Viewing all 15006 articles
Browse latest View live

የወያኔ መንግስት እስካሁን ድረስ በአፋር ህዝብ ላይ ያየውን ትዕግስት እንደ ፊራቻ ወይም አለማወቅ ወሰዶታል

$
0
0

afar
አኩ ኢብን ከአፋር ለዘ-ሐበሻ እንደዘገበው፦

በአፋር ህዝብና በዒሳ ብሄረሰብ መሀከል ለብዙ ዘመናት የቆየው የብዙ ሰዎች ህይዎት ያለፈበት የድምበር ግጭት በብዙ መንግስታት ዘላቂ መፍትሄ ሳያገኝ ለዚህ አሰከፊ ደረጃ ላይ ደርሷል። ይሁንና የአፋር ህዝብና ሶማሊኛ ተናጋሪው የዒሳ ብሄረሰብ አሁንም በኢህአዴግ መንግስት ዘላቂ መፍትሄ አላገኘም። ባለፉት ሁለት አስር አመታት የደቡብ አፋር ነዋሪዎችና ዒሳዎች መሃከል በተከሰተው ደም አፋሳሽ በሆነው ግጭት ከሁለቱም ብሄሮች ብዙ ሰዎች ሞተዋል። ከሶማሌ ክልል ከሺኒሌ ዞን በኮንትሮባንድ ስራ ወደ አፋር ክልል እየተጠጉ እዛ አካባቢ ሲኖሩ የነበሩ የአፋር ነዋሪዎችን በማሸበር የአፋር መሬትን በሃይል መያዛቸውን የሚነገርላቸው ዒሳዎች ከዚህም ባለፈ የብዙ አፋሮችን ግመሎች፣ ከብቶችና ንብረቶች ዘርፈዋል።

ዒሳዎች ቅዱስ ቁርአንን በእጁ ይዞ እኔ ነጹህ ሰው ነኝ አትግደሉኝ ብሎ የለመናቸውን ያልታጠቁ ሙኢምንን ጨምሮ ዕድሜና ፆታ ሳይለዩ የብዙ አፋሮች ህይወት ለሞት ዳረገዋል። ይህ ሁሉ ሲደርስብን ሰላም የሚያስከብርልን መንግሰት በማጣታችን በጣም አዝነናል፣ የኢህአዴግ መንግስትም ሆነ የአፋር ክልል መንግስት እንደ አንድ መንግስት ህብረተሰቦችን በማወያየት ዘላቂ መፍትሄ መስጠት ሲጠበቅበት ግን አልቻለም። አሁን ይባስ ብሎ ለዒሳዎች በአፋር ክልል ውስጥ ልዩ ቀበሌዎች መስጠቱን ሰምተናል። ይህ መላው አፋርን ከጫፍ እስከ ጫፍ ያስቆጣው ወሰን አጥበቀን እንቃወምለን ። ወያነ ለዚህ ወሳኔ ያስፈረማቸውን የአፋር ክልል መሪዎች የአፋር ህዝብን አይወክሉም አናውቃቸውም። የወያኔ መንግስት እስካሁን ድረስ በአፋር ህዝብ ላይ ያየውን ትዕግስት እንደ ፍራቻ ወይም አለማወቅ ወሰዶታል።

በትናንትናው ዕለት ታሕሳስ 2/2007 በአዋሽ የተደረገው ስምምነት የአፋር ሕዝብ መሬቱንም ሆነ አገሩን ማጣቱ እና ለኢሳ የተሰጠ መሆኑን በኢህአዴግ የተረጋገጠ ሰነድ ላይ የአፋርን ሕዝብ የማይወክሉ የአብዴፓ ባለስልጣኖች የፈረሙበት የትልቅ ታሪክ አዋራጆች ቀን ብለን ሰይመነዋል። የአፋር ክልል ማንኛውም ኢትዮጲያዊ በሰላም የሚኖረበት ክልል መሆኑን የሚታወቅ ሲሆን፣ ከወራት በፊት ዒሳዎች በአፋር ክልል በሰላም እንዲኖሩ ተፈቅዶላቸው እኛ የአፋር መሬት ወደ ሶማሌ ክልል ካልተካለልን አሸባሪ እንሆናለን ብለው እየፎከሩ ለነበሩ ዒሳዎች ዛሬ ወያነ እነርሱን ፈርቶ የአፋር መሬት ከሰጣቸው እኛም ሰላም ባጣንበት አገራችን ወያነም ሆነ ነፍሰ ገዳይ የሆኑት የአልሸባብ ተላላኪ ዒሳዎች በአናታችን በሰላም እንዲኖሩ አንፈቅድም!!!!

መብታችን ማስከበር ሽብር ከሆነ እንሆናለን!!
የሚያስተዳድረን ፍትሃዊ መንግስት ከሌለ ሁላችንም ለሞት እንዘጋጃለን!!
ፍትህ ለተጨቆኑ የኢትዮጵያ ህዝቦች!!


Health: ዝንጅብል ለጤና ያለው 10 ጠቀሜታ

$
0
0

genger
ዝንጅብል ውስጡ ባለው የቫይታሚን ሲ፣ የማግንዚየም እንዲሁም ሌሎች ንጥረ ነገሮች ለጤና ከፍተኛ ጥቅም እንደሚሰጥ ይነገራል። ከእነኚህ መካከል አስሩን እነሆ፦
1/ ካንሰርን መከላከል
ከ 17 በላይ ጥናቶች እንደሚጠቁሙት ዝንጅብል የካንሰር እድገትን የሚያቆም ንጥረ ነገር በውስጡ የያዘ በመሆኑ ከ101 በላይ በሽታዎችን ይከላከላል።
2/ ማቅለሸለሸን ያስቆማል
ረጅም ጉዞ ከመጀመርዎ በፊት አንድ ሲኒ የዝንጅብል ሽይ መጠጣት ማስመለስ እና ማቅለሽለሽን የመሳሰሉ ችግሮችን ሊካላከሉ ይችላሉ።
3/ የጨጓራ እና የሆድ ስራን ይሻሽላል
ዝንጅብል የምግብ መፈጨት እንዲሁም የሆድ ጤንነትን የማሻሻል አቅም አለው።
4/ የሰውነት መቆጣትን ይቀንሳል
የመገጣጠሚያ እና የጡንቻ ችግሮች| ካለብዎት ዝንጅብል ፍቱን መድሀኒት መሆኑን ጥናቶች ያሳያሉ። የዝንጅብል ሻይን ከመጠጣት ባለፈ የተቆጡ የሰውነት መገጣጠሚያ አካባቢን በዝንጅብል ማሸትም ጥሩ ማስታገሻ ነው።
5/ የመተንፈሻ አካላት ችግሮችን ይከላከላል
ከጉንፋን ጋር ከተያያዙ የመተንፈሸ አካል በሸታዎች ለመፈወስም ያግዛል።
6/ የደም ዝውውርን ያሻሽላል
በዝንጅብል ሻይ ውስጥ የሚገኙ ቪታሚኖች፣ ማእድናት እና አሚኖ አሲድ ለደም ዝውውር መሻሻል ከፍተኛ ጠቀሜታ ያላቸው ናቸው።
7/ በወር አበባ ጊዜ የሚኖር የሆድ ህመምን ይቀንስል
ሴቶች በወር አበባ ጊዜ የሚኖርን የሆድ ህ|መም ለመቀነስ ሞቅ ባለ የዝንጅብል ሻይ ውስጥ ፎጣን በመንከር ሆድ አካባቢ ማሸት የሚሰማቸውን ህመም ለመቀነስ ያግዛል።
8/ በሽታን የመከላከል አቅምን ይጨምራል
ውስጡ ባለው ከፍተኛ ንጥረ ነገር ምክንያት በሽታ የመከላከል አቅምን ሊጨምር ይችላል።
9/ ጭንቀትን ያስወግዳል
ዝንጅብል ጭንቀትን የማስወገድ አቅም አለው ተብሎ ይነገርለታል ይህም ውስጡ በያዘው ጠንካራ መዓዛ እና ንጥረ ነገሮች ምክንያት ነው።
10/ ለአስም በሸታ
የተደረጉ ጥናቶች እንደሚጠቁሙት ዝንጅብል ከአስም ጋር የተያያዙ ህመሞችን የመቀነስ ባህሪ አለው።

‹‹የኢትዮጵያና የጂቡቲ ሕዝቦች ፍላጎት ከሆነ ውህደትን ተግባራዊ ማድረግ አለብን›› የጂቡቲው ፕሬዚዳንት ኢስማኤል ዑመር ጌሌ

$
0
0

 

የጂቡቲው ፕሬዚዳንት ኢስማኤል ዑመር ጌሌ

የጂቡቲው ፕሬዚዳንት ኢስማኤል ዑመር ጌሌ

ረፖርተር

የጂቡቲው ፕሬዚዳንት ኢስማኤል ዑመር ጌሌ፣ ጥንታዊና ታሪካዊ የሆነው የኢትዮጵያና የጂቡቲ ግንኙነት በአሁኑ ጊዜ ጥልቅ እየሆነ መምጣቱንና አንዱ አገር ለአንዱ አስፈላጊ የሆነበት ደረጃ ላይ መድረሱን ገለጹ፡፡

የሁለቱ አገሮች ሕዝቦች የውህደት ፍላጎት ካላቸውም ይህንኑ ተግባራዊ ማድረግ ያስፈልጋል ብለዋል፡፡

ከኢትዮጵያ የተለያዩ የመገናኛ ብዙኃን የተወጣጡ ባለሙያዎች ባለፈው ሳምንት  ጂቡቲን በጎበኙበት ወቅት፣ ፕሬዚዳንቱ ከጋዜጠኞቹ ጋር አጭር ቆይታ አድርገው ነበር፡፡

በጂቡቲ መንግሥት ግብዣ ወደ አገሪቱ የተጓዙት ጋዜጠኞች ለአምስት ቀናት በነበራቸው ቆይታ ከተለያዩ የመንግሥት ኃላፊዎች የተገነዘቡትን የጂቡቲና የኢትዮጵያ ኢኮኖሚያዊና ማኅበራዊ ቁርኝት ፕሬዚዳንቱ በድጋሚ አረጋግጠዋል፡፡

‹‹የባቡር መስመር ሳይዘረጋ በፊት የኢትዮጵያና የጂቡቲ ሕዝቦች የተቆራኙ ናቸው፤›› ያሉት ፕሬዚዳንት ጌሌ፣ ከኢትዮጵያ ለመጀመሪያ ጊዜ ጂቡቲን ለመጎብኘት የመጣ ሰው ይህንን ቁርኝት ማንም ሳይነግረው መረዳት እንደሚችል አስገንዝበዋል፡፡

‹‹ሁለቱ አገሮች ሽርክ ናቸው፡፡ ያልተባበሩበት ዘርፍ የለም፤›› የሚሉት ፕሬዚዳንቱ፣ ‹‹በኢትዮጵያና በጂቡቲ መካከል ልዩነት አይሰማንም፤›› ብለዋል፡፡

አሁን በየደረጃው የሚታየው ማኅበራዊ፣ ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ትስስር መጨረሻው ምን ይሆናል? ሁለቱ አገሮች ተዋህደው አንድ አገር የመሆን ዕድል አላቸው ወይ? ይኼንንስ እርስዎ እውን ሆኖ ማየት ይፈልጋሉ ወይ? በሚል ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች በሰጡት ምላሽ፣ ‹‹የኢትዮጵያና የጂቡቲ ሕዝቦች ፍላጎት ከሆነ ውህደትን ተግባራዊ ማድረግ አለብን፤›› ብለዋል፡፡

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በዚህ ዓመት ባፀቀደው አዋጅ የጂቡቲ መንግሥት 103,000 ሜትር ኪዮብ ውኃ ከኢትዮጵያ በየቀኑ በነፃ እንዲያገኝ መፍቀዱ ይታወሳል፡፡ ከዚህ በተጨማሪም የኤሌክትሪክ ኃይል በዝቅተኛ ታሪፍ ለጂቡቲ መንግሥት መቅረቡና አሁን እየተሸጠ ካለው የኤሌክትሪክ አቅርቦት በተጨማሪ፣ በአፋር በኩል ተጨማሪ ማስተላለፊያ መስመር ለመዘርጋት የመጨረሻው ዝግጅት ላይ እንደሚገኝ ለማወቅ ተችሏል፡፡ ሁለቱን አገሮች በባቡር ለማገናኘት በጂቡቲ በኩል 98 ኪሎ ሜትር የባቡር ሐዲዱ የመዘርጋቱ ሥራ 60 በመቶ መድረሱን ለመገንዘብ ተችሏል፡፡

በጂቡቲ በኩል ደግሞ ለአፋር ክልል ቅርብ በሆነ ታጁራ በሚባል አካባቢ ለኢትዮጵያ የፖታሽ ማዕድን ኤክስፖርት ማድረጊያ ወደብ በ160 ሚሊዮን ዶላር እየተገነባ ነው፡፡ ይኼንን ወደብ ምክንያት በማድረግም ከመቐለ ታጁራ የሚደርስ የባቡር መስመር ለመዘርጋት በኢትዮጵያ በኩል እየተሠራ መሆኑ ይታወቃል፡፡ ጂቡቲ በወደብ ግንባታ ረገድ ለኢትዮጵያ የኤክስፖርት ዓይነቶች ልዩ ወደቦችን በመገንባት ቅድሚያ ሰጥታ እየሠራች እንደሆነ ለመገንዘብ ተችሏል፡፡ ከላይ እንደተገለጸው ለፖታሽ ኤክስፖርት ግንባታው ከተጀመረው የታጁራ ወደብ በተጨማሪ የኢትዮጵያ የቁም እንስሳት ኤክስፖርት ማድረጊያ ወደብ በዕቅድ ተይዟል፡፡

ከዚህ በተጨማሪም በረዥም ጊዜ ዕቅድ ግሬት ሆርንስ የተባለ የመርከብ ድርጅትና ወደብ ለማቋቋምና ለደቡብ ሱዳን፣ ለኢትዮጵያና አካባቢው አማራጭ ወደብ የመፍጠር ዕቅድ ተይዟል፡፡

‹‹ለመድረስ ከምንፈልግበት በጣም ብዙ ሩቅ ነን፤›› የሚሉት ደግሞ የአገሪቱ የገንዘብና ኢኮኖሚ ሚኒስትር ኤልያስ ሞሳ ዳዋሌ ናቸው፡፡ ሚኒስትሩ አክለውም፣ ‹‹ያለ ኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ዕድገት የጂቡቲ እንቅስቃሴ ጣዕም የለውም፤›› ብለዋል፡፡ የኢትዮጵያ መንግሥት ለጂቡቲ የኃይል አቅርቦት በርካሽ ዋጋ በማቅረቡም 30 በመቶ የኃይል ግዥ ዋጋ መቀነሱን ተናግረዋል፡፡

የመንግሥት ለመንግሥት ግንኙነት ከሞላ ጎደል በየቀኑ መሆኑን የተናገሩት ሚኒስትሩ፣ በሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነት ግን ክፍተት መኖሩን ተናግረዋል፡፡ በጂቡቲ የኢትዮጵያ አምባሳደር ሱሌይማን ደደፎ በበኩላቸው፣ ‹‹የሁለቱ አገሮች ግንኙነት ከዲፕሎማሲያዊ ቋንቋ ባለፈ የሚገለጽ ነው፤›› ብለዋል፡፡

‹‹ሁለቱ አገሮች እየፈጠሩ ያሉት የኢኮኖሚ ውህደት ነው፤›› ያሉት አምባሳደሩ፣ የኢኮኖሚ ውህደት ካለ ደግሞ የፖለቲካ ውህደት እንደሚመጣ ዕምነታቸው መሆኑን አስረድተዋል፡፡

ከዓመታት በፊት ነው፡፡ የአእምሮ ዕድገት ውስንነት ያለባት ሴት አስገድዶ ከደፈራት ታረግዛለች፡፡ የልጇን አባት በውል የማታውቀው ይህችው እናት ከወለደች በኋላ በርካታ ችግሮች ከፊቷ ተጋረጡ፡፡ ገቢ አልነበራትም፡፡

$
0
0

ረፖርተር

ከዓመታት በፊት ነው፡፡ የአእምሮ ዕድገት ውስንነት ያለባት ሴት አስገድዶ ከደፈራት ታረግዛለች፡፡ የልጇን አባት በውል የማታውቀው ይህችው እናት ከወለደች በኋላ በርካታ ችግሮች ከፊቷ ተጋረጡ፡፡ ገቢ አልነበራትም፡፡

በመሆኑም በቂ ገቢ ከሌላቸው ዘመዶቿ ጋር ከጅላ መኖር ግድ ሆነ፡፡ በቂ ምግብና እንክብካቤ የሕፃኗ ችግር ሲሆኑ ገና ድክ ድክ ስትል የገጠማት የሚጥል በሽታ ደግሞ ብዙ መዘዞችን ማስከተሉ አልቀረም፡፡

bcba2c7d61a07f13286612c710db37fe_Lችግሩ በይበልጥ መባባስ የጀመረው ሕፃኗ ዕድሜዋ ለትምህርት ደርሶ መዋዕለ ሕፃናት ከገባች በኋላ ነበር፡፡ ይኸውም ከቤት ወደ ትምህርት ቤት ስትሄድ ወይም ወደ ቤት በምትመለስበት ሰዓት አንዳንዴ ደግሞ እንጨት ለመግዛት በምትወጣበት ጊዜ ድንገት ከሚጥላት በሽታ ጋር ተያይዞ ይገጥማት የነበረው መደፈር ነው፡፡

የሚጥላት በሽታ አልፎላት ከወደቀችበት ስትነሳ ደምና ፈሳሽ ነገር በአካሏ ላይ ለመጀመርያ ጊዜ ማየቷን ሆኖም ትኩረት እንዳልሰጠችውና ለማንም እንዳልተናገረች ታስታውሳለች፡፡ ዕድሜዋ ከፍ እያለ ሲመጣ ለመምህሮቿ ‹‹የደም ፍንጣቂና ነጣ ያለ ፈሳሽ በአካል ላይ ማየት የምን ምልክት ነው፡፡ በጓደኛዬ ላይ ተከስቷል?›› ስትል በተደጋጋሚ ጊዜ ብትጠይቅም ‹‹ይህ ነው›› ከማለት ይልቅ ‹‹ልጅቷን አገናኝንና እናነጋግራት›› ስለሚሏት ነገሩን በዝምታ ታልፈዋለች፡፡

ዕድሜዋ ከፍ እያለ ሲመጣ አካሏ ላይ የምታገኘው ፈሳሽ በመደፈሯ ምክንያት የመጣ እንደሆነ ገባት፡፡ ይሁን እንጂ ማን እንደደፈራት የማወቁ ዕድል አልነበራትም፡፡ ‹‹ራሴን ስቼ ስወድቅ ነው የሚደፍሩኝ፤›› የምትለው ተጠቂዋ ሰብዓዊ ክብሯን የሚጋፉ ወንዶችን ለይታ ማወቅ እንዳልቻለች ትገልጻለች፡፡

የ13 ዓመት ልጅና ዘጠነኛ ክፍል ስትደርስ በጤናዋ ላይ ካለው ችግርና ከሚገጥማት የአስገድዶ መድፈር ጥቃት በተጨማሪ እሷንና እናቷን የሚያስተዳድሩት ዘመዶቿ ኑሮ ከበዳቸው፡፡ ‹‹አንዳንዴ ከቤት ውስጥ የሚላስ የሚቀመስ ይጠፋል›› የምትለው ታዳጊዋ፣ ነገሮችን በውል ማገናዘብ የማትችለውን እናቷን ነፍስ ለመታደግ ‹‹አንዴ ከአንዱ ሱቅ የሚበላ ተበድሬ አመጣለሁ፡፡ አንዴ ደግሞ ከሌላኛው ሱቅ ተበድሬ እያመጣሁ 49 ብር ዕዳ ደረሰብኝ፡፡ ከዚያ ‹ክፈይን› እያሉ ሲጨቀጭቁኝ መደበቅ ጀመርኩ፤›› በማለት ይህ አጋጣሚ ሌላ ችግር ፊት ለፊት እንድትጋፈጥ ምክንያት እንደሆነ ተናግራለች፡፡

እንደ እሷ ገለጻ፣ በቤት ውስጥ ያለው የኑሮ ችግርና ታዳጊዋ የገባችበትን ዕዳ በቅርበት ያስተዋለው በአያት በኩል የምትዛመደው ግለሰብ፣ ገንዘቡን እንደሚሰጣት ሲነግራት ደስታዋ ወደር አልነበረውም፡፡ የተባለውንም ገንዘብ ለመቀበል ከምትኖርበት ቤት ብዙ ወደ ማይርቀው የግለሰቡ መኖሪያ ቤት አመራች፡፡ የጠበቃት ነገር ግን ፍፁም የተለየ ነበር፡፡

ታዳጊዋ እንደ ከዚህ ቀደሙ ራሷን ስታ አልወደቀችም፡፡ ገንዘብ ሊሰጣት ቃል የገባላት ዘመዷ ሲደፍራት እያንዳንዱን ሁኔታ ታስታውሳለች፡፡ ‹‹ለመጀመርያ ጊዜ የደፈረኝን ሰው አየሁ፡፡ ሁሌም ይደፍረኝ የነበረው እሱ መሰለኝ፡፡ ዕድሌን እያማረርኩ አለቀስኩኝ፤›› በማለት በወቅቱ የነበረውን ሁኔታ ታስታውሳለች፡፡

ስለደረሰባት ጥቃት ግን ለማንም ከመናገር ተቆጥባ ነበር፡፡ ተፈጥሮ ግን ጊዜውን ጠብቆ ከማሳበቅ አልተቆጠበም፡፡ እንደሌላው ጊዜ ተደፍራ ብቻ አልቀረችም፡፡ እርግዝናም ተከተለ፡፡ የሆዷን መግፋት በጥርጣሬ የተመለከቱት ዘመዶቿ በጥያቄ አጣደፏት፡፡ ዱላ ዘለፋና ከትምህርት ገበታ መቅረት፣ ተደፍራ የማርገዟን ዕውነታ ስትናገር አሳዳሪ ዘመዶቿ የወሰዱባት ዕርምጃዎች ነበሩ፡፡

ነገር ግን በድርጊታቸው ብዙም ሳይገፉ ሐሳባቸውን ቀይረው ወደ አዲስ አበባ ፖሊስ ጣቢያ ወስደዋት ስለ ሁኔታው ለፖሊስ አስረዱ፡፡ ፖሊሶችም ታዳጊዋ ለተጨማሪ ምርመራ ቀጥታ ወደ ጋንዲ ሆስፒታል እንድትሄድ አዘዙ፡፡ ቀጥሎም ጥቃት ፈጻሚው ለምርመራ ማረፊያ ቤት እንዲቆይ ተደረገ፡፡

ከዚህ በኋላ ግን ከቤተሰቦቿ ጋር የነበራት ቆይታ ከሳምንት ሊበልጥ አልቻለም፡፡ በዚህ ሁኔታ ብዙ መግፋት ስላልቻለች ችግሯን ለፖሊስ አስረዳች፡፡ እሷን የመሰሉ ጥቃት የደረሰባቸው በሚኖሩበት የተጠቂ ሴቶች መጠለያ ማኅበር እንድትቀላቀልም ተደረገ፡፡

ወደ መጠለያው ከመጣች አሥር ወር አልፏታል፡፡ ልጇንም በሰላም ተገላግላለች፡፡ ይሁን እንጂ ስለተፈጸመባት ወንጀል የማጣራት እንቅስቃሴው ምን ያህል እንደተጓዘ አታውቅም፡፡ ‹‹አብረውኝ የሚኖሩ ጥቃት የደረሰባቸው ሴቶች በየጊዜው ለምስክርነት ፍርድ ቤትና ፖሊስ ጣቢያ ሲጠሩ አያለሁ፡፡ እኔ ግን አንድም ቀን ተጠርቼ ሄጄ አላውቅም፤›› በማለት የእሷ የፍትሕ ጥያቄ እልባት ሳያገኝ የቀረ እንደሆነ ትገምታለች፡፡

‹‹የመጨረሻ ፍርድ ካልተሰጠ ካለሁበት መጠለያ መውጣት አልችልም›› የምትለው ታዳጊዋ ክሱ ምን ደረጃ ላይ እንደደረሰ ብታውቅና ያቋረጠችውን ትምህርቷን በመቀጠል ልጇንና እናቷን የምታስተዳድርበት ሁኔታ ቢፋጠንላት ምርጫዋ እንደሆነ ትናገራለች፡፡

እሷ በምትኖርበት መጠለያ ውስጥ 83 የሚሆኑ እናቶች ሲኖሩ ከነዚህ ውስጥ ብዙዎቹ ተደፍረው ወደ ማዕከሉ የመጡ ናቸው፡፡ 42 የሚሆኑ በማዕከሉ የሚኖሩ ሕፃናትም ተገደው የተደፈሩ እናቶች የወለዷቸው ናቸው፡፡ መኖሪያቸው በሚስጥር የተያዘ በመሆኑ ወደ ውስጥ ለመዝለቅ ብዙ ቅድመ ሁኔታች አሉት፡፡ ለዚህም ዋነኛው ምክንያት በመጠለያው የሚኖሩ ሴቶች የዓቃቤ ሕግ ምስክሮች ሲሆኑ ከተከሳሽ በኩል የሚደርስባቸውን የማስፈራራትና ተጨማሪ ጥቃት ለመከላከል እንደሆነ ይናገራሉ፡፡

መጠለያው ለዓመታት በርካታ የጥቃት ሰለባ የሆኑ እንስቶች ማረፊያ ሆኖ ቆይቷል፡፡ በየጊዜውም የሚደፈሩ ሴቶች ቁጥር እያየለ በመምጣቱ ምንም እንኳ የጀመሩት የሕግ ክትትል ፍጻሜ አግኝቶ ወደ የመጡበት የሚመለሱ ሴቶች ቢኖሩም በየቀኑ የሚመጡ የጥቃት ሰለባዎች ሞልተዋል፡፡ እስከ ሦስት ዓመት ድረስ የቆዩ ሴቶችም ይገኙበታል፡፡

ከዓመታት በፊት በኦሮሚያ ክልል አርሲ አካባቢ የምትኖረው ታዳጊ እንደወትሮዋ የገብስ ማሳውን እያቆራረጠች ወደ ትምህርት ቤት መጓዝ ጀምራለች፡፡ ነገሮች ግን እንደቀድሞው ሊሆኑ አልቻሉም፡፡ ድንገት መልካቸውን ቀየሩ፡፡ እንደ እሷ ገለጻ፣ ማሳውን አቋርጦ የሚያልፈው ግለሰብ ባለ በሌለ ኃይሉ ግጥም አድርጎ ያዛት፡፡ ለማምለጥ ያደረገችው መወራጨት ከምንም አላዳናትም፡፡ አስገድዶም ደፈራት፡፡ ግለሰቡ ግን በዚህ ብቻ ሊለቃት ፈቃደኛ አልነበረም፡፡ ‹‹ለሰው እንዳትናገር›› በሚል ሰበብ በስለት አንገቷን አርዷት ተሰወረ፡፡ የታዳጊዋ ሕይወት ግን በቀላሉ አላለፈም፡፡ ይልቅኑ የአካባቢው ሰዎችና ጥቃት የደረሰባቸው ሴቶች መጠለያ ማኅበር ባደረጉት ርብርብ ሕይወቷ ተረፈ፡፡ የምትተነፍሰው በተገጠመላት አርቴፊሻል መሣሪያ ሲሆን፣ ሦስት ዓመት ያህል በመለጠያው ቆይታለች፡፡

ግለሰቡም ከተሰወረበት ተገኝቶ የሕግ ፍርደኛ ሊሆን በቅቷል፡፡ ይሁን እንጂ የተሰጠው ፍርድ በእሷ ላይ ከደረሰው ጉዳት አንፃር ዝቅተኛ ነው በሚል እንደተከፋች በማዕከሉ የሚገኙ የሥነ ልቦና ባለሙያዎች ይገልጻሉ፡፡ ባደረሰባት ከፍተኛ ጉዳትም እንደማንኛውም ሰው ተንቀሳቅሳ መሥራት አትችልም፡፡ ለእሷ ከደረሰባት ጉዳት አንፃር በበደላት ላይ የተፈረደው እሥራት ምንም ማለት አይደለም፡፡

ሌላዋ በማዕከሉ የምትገኘው የ18 ዓመት ታዳጊ ስትሆን በአክስቷ የልጅ ልጅ አማካይነት በደረሰባት የአስገድዶ መደፈር ጥቃት ክስ በማቅረቧ ከአክስቷ ጋር መቆየት አልቻለችም፡፡ ስለዚህም ወደ ማዕከሉ መምጣት ብቸኛ አማራጯ ነበር፡፡ ወደ ማዕከሉ የመጣችው በ2005 ዓ.ም. ሲሆን፣ በወቅቱ ከሁለት ቀናት በኋላ እንደምትወጣ ተነግሯት ነበር፡፡ ይሁን እንጂ በፍርድ ቤት ተገኝታ የምስክርነት ቃሏን ብትሰጥም ጉዳዩ እስካሁን ድረስ መቋጫ ስላልተገኘለት ከትምህርቷም ሆነ ከሌሎች ማኅበራዊ ሕይወቷ ታቅባ በማዕከሉ መቀመጥ ግድ ሆኖባታል፡፡

ወጣት ባዩሽ ጋዲሳ በመጠለያ ማዕከሉ ለሚመጡ ሴቶች የሕግ አገልግሎት ክትትል ኦፊሰር ናት፡፡ እንደ እሷ ገለጻ፣ ጥቂት የማይባሉ ክሶች ውሳኔ ሳያገኙ ለዓመታት ይንጓተታሉ፡፡ በሌላ በኩልም በወንጀለኛው ላይ የሚተላለፉት ፍርዶች አነስተኛ ይሆናሉ፡፡ ሁኔታው ብዙ ጊዜ የሚስተዋል በመሆኑ ተጠቂዎቹን ፍትሕ የማግኘት ተስፋ እያጨለመው እንደሚገኝ ትገልጻለች፡፡

‹‹እኛ አደራ ተቀባዮች ነን›› የምትለው ባዩሽ፣ ተጠቂዎቹ ከማዕከሉ ዕውቅና ውጪ መንቀሳቀስ እንደማይችሉ ትናገራለች፡፡ ‹‹መውጣት ቢፈልጉ እንኳን እኛ ከጎናቸው መሆን ይጠበቅብናል›› ትላለች፡፡ ይህንንም ተከትሎ የመጨረሻ ፍርድ ሳያገኙ ለዓመታት በሚቆዩበት ሁኔታ የውጪው ዓለም ስለሚናፍቃቸው ያለመረጋጋትና የመረበሽ ስሜት ይፈጥርባቸዋል፣ በዚህም ምክንያት ማዕከሉን የሚረብሹበት አጋጣሚዎች መኖራቸውን ትናገራለች፡፡

በሴቶች ዙሪያ በሚፈጸሙ ጥቃቶች ላይ የሚሰጡት ፍርዶች አነስተኛና ኢፍትሐዊ ናቸው፣ በመሆኑም የወንጀል ሕጉ እንደገና እንዲከለስና የሚጣለው ቅጣትም ከባድ እንዲሆን የሚጠይቅ ደብዳቤ በቅርቡ ለጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ ከኢትዮጵያ ሴቶች ማኅበራት ቅንጅት መላኩ የሚታወስ ነው፡፡

ይህንንም ተከትሎ በርካታ ሐሳቦች ሲሰነዘሩ ቆይተዋል፡፡ በጉዳዩ ሪፖርተር ያነጋገራቸው የኢትዮጵያ የሕግ ባለሙያ ሴቶች ማኅበር የሥራ አስፈጻሚ ዳይሬክተር ወ/ሮ ዜናዬ ታደሰ፣ በፍርድ ቤት በሚሰጡ ፍርዶች ፍትሐዊነት ላይ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል፡፡

እንደ እሳቸው ገለጻ፣ በወንጀል ሕጉ የተቀመጡት ቅጣቶች ይህን ያህል የሚያስከፋ አይደሉም፡፡ ይሁን እንጂ የሚሰጡ ፍርዶች ብዙ ጊዜ ፍትሐዊነት የጎደላቸው ሆነው ይታያሉ፡፡ ለዚህም ዋነኛው ምክንያት ዳኝነት ላይ የሚቀመጡት ግለሰቦች ስለ አስገድዶ መድፈር የሚኖራቸው አመለካከት፣ ማስረጃ ላይ የሚኖራቸው ዕይታ፣ ድርጊቱን እንዴት ይመለከቱታል? ውጤቱንስ እንዴት ያዩታል? የሚለው መሠረታዊ ነገር የዳኞችን ግላዊ አመለካከት የያዘ ፍርድ እንዲሰጡ ያደርጋቸዋል፡፡ በዚህም ምክንያት በቂ መረጃ እያለ መረጃ የለም በሚል ኢፍትሐዊ ውሳዎኔች ይሰጣሉ፡፡ ተጠርጣሪውን በአነስተኛ ዋስ መልቀቅና እንዲያመልጥ መንገድ መክፈት፣ አንዳንድ ቅጣቶች ላይ እላግባብ ማቅለያ በማድረግ፣ ኢፍትሐዊ ፍርድ ሲሰጥ ይታያል ይላሉ፡፡

ይህንን በተመለከተም በአንድ ወቅት በፍርድ ሒደት ያስተዋሉትን እንዲህ ያስታውሳሉ፡፡ ‹‹ወንጀሉ ስለመፈጸሙ ሙሉ መረጃ ነበረ፡፡ ነገር ግን ዳኛው ፍርዱን ሲያስተላልፉ ‹ሴቶች በጉያቸው እሳት ይዘው የሚዞሩ ፀብ አጫሪዎች ናቸው› የሚል ጽሑፍ አስፍሮ ወንጀለኛውን በነፃ ለቀቀው›› ይላሉ፡፡

ስለዚህም በፍርድ ቤት የሚሰጡ ፍርዶች ፍትሐዊ እንዲሆኑ ሕጉ ሳይሆን፣ በቅድሚያ መስተካከል ያለበት በፍርድ ላይ የሚስተዋሉ የግላዊ አመለካከቶች መቅረት እንደሆነ ወ/ሮ ዜናዬ በአጽንኦት ይገልጻሉ፡፡

በመረጃ እጥረት ምክንያት ወደ ፍርድ ቤት ሳይቀርቡ የሚቀሩ ኬዞችን በሚመለከት ማኅበረሰቡ ያየውን ሁሉ በመመስከር ለመረጃ መጠናቀር የበኩሉን ቢያበረክት፣ ችግሩ እልባት እንደሚያገኝ ገልጸዋል፡፡ ‹‹በወንጀለኞች ላይ የሚተላለፉ ፍርዶች በማኅበረሰቡ ላይ አስተማሪና መቀጣጫ ሆነው ማለፍ አለባቸው›› ሲሉም ያክላሉ፡፡

አንድነት በጥቂት ቀናት ውስጥ የጠራው ጠቅላላ ጉባኤ በስክት ተጠናቋል

$
0
0

አንድነት በጥቂት ቀናት ውስጥ የጠራው ጠቅላላ ጉባኤ በስክት ተጠናቋል፤ የፓርቲው ተ/ም/ፕሬዝዳንት አቶ ተክሌ በቀለ የጉባኤውን የመዝጊያ ንግግር በማድረግ ላይ ናቸው፡፡ አቶ ተክሌ በንግግራቸው አንድነት በብሔርም ሆነ በህብረብሔር ፓርቲዎች ጋር አብሮ ለመስራት መዘጋጀቱን እንዲሁም ከአንድነት ጋር ተመሳሳይ ፕሮግራም ላላቸው ፓርቲዎች ሁሉ የውህደት ጥያቄ አቅርበዋል፡፡ አቶ ተክሌ አክለውም አንድነት የ2007 ምርጫን በአሸናፊነት ለመወጣት እየሰራ እንደሚገኝ ተናግረዋል፡

10801506_830102687048482_9079775044209922653_n

10847773_830102467048504_99358985024134609_n

አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ከትላንት ጀምሮ እያካሄደ ባለው ጠቅላላ ጉባኤ ላይ ስልጠና እየተሰጠ ነው፤ በዛሬው መርሀ ግብር በሀገሪቱ ነባራዊ ሁናቴዎች(የአርሶ አደሩ ፤የከተማው ነዋሪ፤የባለሐብቱ ሁናቴ) በዳግማዊ ተሰማ የተማሪውና የምሁሩ ሁናቴ በጋዜጠኛ አናንያ ሶሪ የአንድነት የምርጫ ስትራቴጂ ግብ በፓርቲው ፕሬዝዳንት አቶ በላይ ፈቃዱ ቀርቦአል፡፡ በመቀጠልም የስልጠናው ተሳታፊዎች ጥያቄና አስተያየት በመስጠት የጠዋቱ ስልጠና ተጠናቆ፣ የአንድነት ፓርቲ ም/ፕሬዝዳንት የተከበሩ አቶ ግርማ ሰይፉ በምርጫ ስትራቴጂ ዙሪያ ስልጠና ሰጥተዋል፡፡ በመቀጠልም የአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ የህግና ሰብአዊ መብት ምክትል ሰብሳቢ የሆኑት አቶ ገበየሁ ይርዳው የአባላት መብትና ግዴታ ከፓርቲው ደንብና ከፖለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባ አዋጅ አንጻር ስልጠና ሰጥተዋል ነው፡፡ በአሁኑ ሰዓት መድረኩ ለውይይት ክፍት ሆኖ ውይይት እየተደረገ ይገኛል፡፡

10689712_742890089129261_399577300201419677_n

የፓርቲው ተ/ም/ፕሬዝዳንት አቶ ተክሌ በቀለ የጉባኤውን የመዝጊያ ንግግር በማድረግ ላይ ናቸው፡፡ አቶ ተክሌ በንግግራቸው አንድነት በብሔርም ሆነ በህብረብሔር ፓርቲዎች ጋር አብሮ ለመስ…

1957988_742880462463557_856926840329555149_n

በአሁኑ ሰዓት ጉባኤው ለጋዜጠኞችና ለክብር እንግዶች ክፍት ሆኗል፡፡ አንድነት ፓርቲ ለዞንና ለወረዳ አመራሮች ያዘጋጀው ስልጠና በስኬት ተጠናቋል፡፡ በአሁኑ ሰዓት ጉባኤው ለጋዜጠኞችና ለክብር እንግዶች ክፍት ሆኗል፡

1501666_742879365797000_2313086908782721306_n

በአሁኑ ሰዓት ጉባኤው ለጋዜጠኞችና ለክብር እንግዶች ክፍት ሆኗል፡፡ አንድነት ፓርቲ ለዞንና ለወረዳ አመራሮች ያዘጋጀው ስልጠና በስኬት ተጠናቋል፡፡ በአሁኑ ሰዓት ጉባኤው ለጋዜጠኞችና ለክብር እንግዶች ክፍት ሆኗል፡

 

10857738_830102633715154_3545412742057696770_n

 

የጉባኤውን መዝጊያ በማስመልከት የተለያዩ የሙዚቂ ዝግጅቶች እየቀረቡ ነው፡፡

1979760_830121140379970_5791000346813560187_n

10850209_830120993713318_7821501057591246485_n

10429209_830121313713286_3649092189897821075_n

የጉባኤውን መዝጊያ በማስመልከት የተለያዩ የሙዚቂ ዝግጅቶች እየቀረቡ ሲሆን በየጣልቃው የአንድነት ፓርቲ ድጋፍ ሰጪዎች ከመላው ዓለም የድጋፍ መልዕክት እያስተላለፉ ነው፡፡

በአሁኑ ሰዓት ጉባኤው ለጋዜጠኞችና ለክብር እንግዶች ክፍት ሆኗል፡፡ አንድነት ፓርቲ ለዞንና ለወረዳ አመራሮች ያዘጋጀው ስልጠና በስኬት ተጠናቋል፡፡ በአሁኑ ሰዓት ጉባኤው ለጋዜጠኞችና ለክብር እንግዶች ክፍት ሆኗል፡፡

10606170_742879392463664_586079173473258862_n 10698475_829409667117784_3680643737158512454_n 10696378_830102643715153_5337011227327904207_n 10868059_742890132462590_6829345466535035832_n 10857738_830102633715154_3545412742057696770_n 10391385_742367799181490_9096613242778417442_n

10698475_829409667117784_3680643737158512454_n

 

በቅስቀሳው ወቅት የታሰሩት አመራሮችና አባላት አሁንም አልተፈቱም

$
0
0

ነገረ ኢትዮጵያ

10687129_627440187381643_6931792570194490039_nለ24ቱ ሰልፍ ቅስቀሳ ላይ እያሉ የታሰሩት ማቲያስ መኩሪያ የሰማያዊ ፓርቲ የአዲስ አበባ ስራ አስፈጻሚ ህዝብ ግንኙነትና የምርጫ ጉዳይ ኃላፊ፣ ባህረን እሸቱ የምርጫ ጉዳይ ቋሚ ኮሚቴ ኃላፊ እንዲሁም ሲሳይ ዘርፉ እስካሁን ድረስ አልተፈቱም፡፡ ባህረን እሸቱና ማቲያስ መኩሪያ ከ30 በላይ እስረኞች ሶስት በአራት በሆነ ክፍል ታጭቀው በሚታሰሩበት ወረዳ 9፤ እንዲሁም ሲሳይ ዘርፉ ላዛሪስት በሚባል እስር ቤት ታስረው የሚገኙ ሲሆን ከፍተኛ በደል እየደረሰባቸው እንደሚገኝ ተገልጾአል፡፡

ሶስቱም ታሳሪዎች ‹‹ለህገ ወጥ ሰላማዊ ሰልፍ በመቀስቀስ›› በሚል ክስ ቀረበባቸው ሲሆን በሰላማዊ ሰልፉ ወቅት የታሰሩት አመራሮች፣ አባላትና ተሳታፊዎች እነዚህ እስረኞች ላይ ከቀረበው በበለጠ ‹‹ህገ መንግስቱን በመናድ›› በሚል ክስ ተከሰው 14 ቀን ቀነ ቀጠሮ ከተሰጠባቸው በኋላ ቀድመው መፈታታቸው ይታወቃል፡፡

 

bb

በአዳር ሰልፉ ወቅት ከፍተኛ ድብደባ ከደረሰባቸው መካከል የሰማያዊ ፓርቲ አባል የሆነው ቡልቻ አባ ኑራ አንዱ ነው፡፡ ይህ ከተደበደበ ከ8 ቀን በኋላ የተነሳ ፎቶ ግራፍ ነው፡

ጀግኖችን እያሰብን የበኩላችንን እንወጣ!! በመስዋዕትነት ነፃነት ይረጋገጣል፤ ሰላም ይሰፍናል። (በስደት የኢትዮጵያ መምህራን ማህበር አባላት አስተባባሪ)

$
0
0

teachers associationመምሀር የኔሰው ገብሬ በዳውሮ ከተማ ነዋሪና ትጉህ መምህር ነበር። እንደማንኛውም አገር ወዳድና የወገን ተቆርቋሪ እርሱም የወያኔ/ኢህአዴግ ሥርዓተ መንግሥት በሕዝብ ላይ የሚያደርሰውን ገደብ የለሽ ሰቆቃ መቀበል ባለመቻሉ ፣ በአንፃሩ በተቃውሞ አቋሙን በአደባባይ የሚገልጽና ይህ እኩይ ድርጊት እንዲቆም ታግሎ ለማታገል በጽናት ስለቆመ የሥርዓቱ ሰለባ ሆነ። እስራቱና እንግልቱ አልበቃ ብሎ ከሥራ መደቡም ተገለለ ። በዚያው ላይ ፍትህ ለማግኘት የሚያስብ ሕሊናና የሚሰማ ጆሮ እንደሌለ ተረድቶ ለአሰቃዩትም ለአጠቃላይ ሕዝቡም መራር መልእክት ያስታላልፋል ብሎ ያሰበውን መስዋዕትነት መርጦ ራሱን በጋዝ አንድዶ ሕዳር 1 ቀን 2004 ዓ.ም መስዋዕት ሆነ። ይህ ተግባሩ ቀደም ሲል ለአገር አንድነትና ለሕዝብ ሉዓላዊነት ፣ ለመምህሩ መብትና ጥቅም መከበር ሲታገሉ መስዋዕት የሆኑትን፣ በእስራት የማቀቁትን፣ ከእናት አገራቸው ተሰድደው በባዕድ አገር ያለውዴታቸው የእንግልትና የናፍቆት ኑሮ የሚገፉትን መምህራን፣ የሙያ ማህበሩ የኢመማ መሪዎችን፣ ደጋፊዎቻቸውንና ተባባሪዎቻቸውንም የሚያስመካ አንጸባራቂ መስዋዕትነት ሆኖ አልፏል። መቼም ቢሆን ነፃነት ያለመስዋዕትነት ተገኝቶ አያውቅም። በሕዝቡ ጫንቃ ላይ ተፈናጦ የሚገኘውን ጨካኙን፣ ዘረኛውን፣ ግፈኛውን፣ —-  [ሙሉውን ለማንበብ እዚህ ይጫኑ]—–

 

 

የመድረክ ሰለማዊ ሰልፍ ተጠናቀቀ::

$
0
0

Minilik Salsawi (ምንሊክ ሳልሳዊ) :

የመድረክ የወጣቶች ክንፍ ከፖሊስ እና ከፀጥታ አካላት እጅና ጓዋንት ሆኖ የክትትል፤ የኢንተለጀንስ እና የቁጥጥር ስራውን በአግባቡ እንዲሚወጣ ለመግለፅ እንፈልጋልን፡፡ የሚል የህዝብ ግንኙነት ስራ ትዝብት ውስጥ የጣለው የመድረክ ፓርቲ ከገንፍሌ ተነስቶ፣ በኣዋሬ ኣልፎ በየካ ክፍለ ከተማ የሚገኝ ኳስ ሜዳ መጨረሻው ያደረገው ሰለማዊ ሰልፍ ተጠናቀቀ።

10411210_1519465441657186_7328125686046851094_nበዘጠኙ ፓርቲ ላይ የደረሰውን እስር ድብደባ እና እንግልት እንዳላወገዘ የሚነገርለት መድረክ ፓርቲ የጠራው ሰላማዊ ሰልፍ ሁለት ሺህ የሚጠጋ የኣዲስ ኣበባ ኑዋሪ የተሳተፈበት ሰልፍ በወጣቶች የመድረክ ኣመራር፣ የሴቶች ተወካይ፣ ኣቶ ቡልቻ ሚደቅሳና የወቅቱ የመድረክ ሊቀመንበር ፕሮፌሰር በየነ ዼጥሮስ ባሰሙት ንግግሮች ተጠቃሏል።
ሰለማዊ ሰልፉ የኢህኣዴግ መንግስት ሊያርማቸው የሚገቡ፣ መመቻቸት ያሉባቸው ፖለቲካዊ ምህዳር፣ መወገድ ያለበት የፀረ ሽብር ህግ ፣ ምርጫው ፍትሃዊ እንዲሆን ሊያደረጉ የሚገቡ ስራዎች እንዲሰሩ፣ በየቦታው እያጋጠመ ያለው ዓፈና፣ እስርና እንዲሁም ግድያዎች እንዲቆሙ ጥሪ ቀርበዋል።

የመድረክ ኣመራሮችና ወጣቶች እየመሩት የተካሄደው የሰለማዊ ሰልፉ ዓላማዎች የምያንፀባርቁ መፈክሮች በወጣቶች ኣባላት ተነበዋል። ከመፈክሮቹ

1- ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት በነፃና ፍትሐዊ ምርጫ እንጂ በአስመሳይ ፕሮፓጋንዳ፣ በኃይልና በተጽኖ አይገነባም!!
2- የሀገራችን ችግሮች በነፃና ፍትሐዊ ምርጫ በሚገለጽ የሕዝብ ውሳኔ እንጂ በኃይል እርምጃ አይፈቱም!!
3- ከምርጫ በፊት የምርጫ ውድድር ሜዳው የሚስተካከልበት ውይይትና ድርድር እንዲካሄድ አጥብቀን እንጠይቃለን!!
4- በማስመሰያ ምርጫ በየአምስት አመቱ ሕዝብን ማታለልና ሀብቱን ማባከን ይቁም!!
5- የማስመሰያ ምርጫ ለማካሄድ ለሚባክነው የሀገርና የሕዝብ ሀብት ኢህአዴግ ተጠያቂ ነው!!
6- ነፃና ፍትሐዊ ምርጫ በሌለበት ሁኔታ የሕዝብ የሥልጣን ባለቤትነት እውን ሊሆን አይችልም!!
7- ሕዝባችን በ1ለ5 መረብ አፈናና ቁጥጥር ከሚካሄድ የምርጫ ድምጽ አሰጣጥ ነፃ እንዲሆን እንጠይቃለን!!
8- ያለገለልተኛ የምርጫ አስተዳደርና ያለገለልተኛ የምርጫ ታዛቢ ታአማንነት ያለው ምርጫ ሊኖር አይችልም!!
9- ገለልተኛ የምርጫ ቦርድ በፖለቲካ ፓርቲዎች ተሳትፎ ይቋቋም!!
10- በካድሬዎች የሚከናወን የምርጫ አስፈጻሚነትና ታዛቢነትን አንቀበልም፣ እናወግዛለን!!
11- ነፃ የሀገር ውስጥና የውጭ ሀገር ታዛቢዎች ምርጫውን በነፃነት የሚከታተሉበትና የሚታዘቡበት ሁኔታ
እንዲመቻች እንጠይቃለን!!
12- በምርጫ ወቅት በታጠቀ ኃይል በሕዝባችን ላይ የሚፈጸም ማስፈራሪያና ወከባን እናወግዛለን!!
13- በሰላማዊ ተቃዋሚ ፓርቲ አባላት ላይ የሚካሄድ እስራትና ወከባ በአስቸኳይ ይቁም!!
14- ኢህአዴግ በመንግሥት ሀብትና ንብረት የሚያከሄደውን ሕገወጥ የምርጫ ዘመቻ እናወግዛለን!!
15- የጸጥታ ኃይሎች የሕዝብ አገልጋዮች እንጂ ሕዝብን ማስፈራሪያና ማሸማቀቂያ መሆን የለባቸውም!!
16- ያልተሟላ የምርጫ ሥነምግባር ኮድ ነፃና ፍትሐዊ ምርጫ ለማካሄድ አያስችልም!!
17- ከድምጽ መስጫ ጣቢያዎች የተቃዋሚ ፓርቲ ታዛቢዎችን ማባረር የሕዝብን ድምጽ ለመስረቅ ስለሆነ በአስቸኳይ
እንዲቆም እንጠይቃለን!!
18- የሕዝብን ድምጽ መዝረፍ ዴሞክራሲን መገንባት ሳይሆን መቅበር ነው!!
19- የምርጫ ጣቢያዎች ከአስተዳደር አካላትና ከታጣቂ ሠራዊት ተጽኖና አፈና ነፃ ይሁኑ!!
20- በምርጫ ወቅት በምርጫ ጉዳዮች ፈጣን ውሳኔ የሚሰጡ ነፃና ገለልተኛ ዳኞች በየደረጃው እንዲኖሩ እንጠይቃለን!!
21- ሰላማዊ ተቃዋሚዎችን ማሰር፣ ማሰቃየትና መግደል ሕዝባችን በዴሞክራሲያዊ ምርጫ የሥልጣን ባለቤት ለመሆን
የሚያካሄደውን ትግል አይገታም!!
22- ሀሳብን የመግለጽ ሕገመንግስታዊ መብታቸውን በመጠቀማቸው የታሰሩ የሕልና እስረኞች በሙሉ በአስቸኳይ ይፈቱ!!
23- በግፍ የታሰሩ ሰላማዊ የተቃዋሚ ፓርቲ አባላት፣ ጋዜጠኞችና የሙስሊሙ ማሕበረሰብ መፍትሔ አፈላላጊዎች በአስቸኳይ ይፈቱ!!
24- የፀረ-ሽብር ሕጉን ለፖለቲካ ዓላማ መጠቀሚያ ማድረግን እናወግዛልን!! ሕገ-መንግሥታዊ መብትን በማይጥስ
ሁኔታ በአስቸኳይ እንዲሻሻልም እንጠይቃለን!!
25- የመንግሥት መገናኛ ብዙሃን ለገዥው ፓርቲ የሚያሳዩትን ወገንተኝነት በአስቸኳይ ያቁሙ!!
26- ሁሉም ፓርቲዎች በሕጋዊና ፍትሐዊ አግባብ ከመንግሥት በጀት ድጋፍ የሚያገኙበት ሥርዓት እንዲኖር አጥብቀን እንጠይቃለን!
27- በነፃነት የመሰብሰብና የመደራጀት መብታችን ይከበር!!
28- የአንድ አምባገነን ፓርቲ ሳይሆን ትክክለኛ የመድበለ ፓርቲ ሥርዓት እንሻለን!!
29- ኢህአዴግ ለሕገመንግሥትና ለሕግ ተገዥ በመሆን ለነፃ ምርጫ እራሱን እንዲያዘጋጅ እንጠይቃለን!!
30- የሕግ የበላይነት ባልተከበረበት ሁኔታ ዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ለመገንባት አይቻልም!!
31- የኑሮ ውድነቱና የተጎሳቆለው የሕዝባችን ሕይወት የኢህአዴግ የኢኮኖሚና ማሕበራዊ ፖሊሲ ውጤቶች ናቸው!!
32- በወገንተኝነትና በአድልኦ በሕዝባችን ላይ የሚጫን ግብር በአስቸኳይ ይስተካከል!!
33- በልማት ስም በሕገወጥና ግብታዊ በሆነ መንገድ ሕዝብን ማፈናቀልና ለችግር ማጋለጥ እንቃወማለን!!
34- የመሬት ወረራ ይቁም!!
35- በሙስና የተዘረፈው የሕዝብ ሀብት ለሕዝቡ ይመለስ!! ሙሰኞችም ለፍርድ ይቅረቡ!!
36- የውኃ፣ የማብራት፣ የትራንስፖርትና የስልክ አገልግሎቶች ችግሮቻችን በአስቸኳይ መፍትሔ እንዲሰጣቸው እንጠይቃለን!!
37- የአህአዴግ አገዛዝ በሐይማኖቶች የውስጥ ጉዳዮች የሚፈጽማቸውን ጣልቃ ገብነቶች እናወግዛለን!!
እነዚህ መፈክሮች ለመላ ዓለም ይሰራጫሉ ተብለው ይጠበቃል።


Health: 12ቱ የኦቾሎኒ አስደናቂ የጤና ጠቀሜታዎች

$
0
0

ይህ ጽሁፍ በዘ-ሐበሻ ጋዜጣ ታትሞ የወጣ

የስኳር በሽተኛ ከሆኑ ወይም ከፍተኛ የደም ግፊት የሚያስቸግርዎ ከሆነ ኦቾሎኒ ይጠቅምዎታል፡፡ በናያሲን (ቫይታሚን ቢ3) የበለፀገ ነው፡፡ ይህም ጎጂውን የኮሌስትሮል አይነት መቀነስ የጠቃሚውን መጠን ይጨምራል፡፡ ኦቾሎኒ በደም ቅዳዎች ላይ ዕጢዎችን እንዳይፈጠሩ የሚከላከለውን እና በአብዛኛው ከቀይ ወይን ጋር የሚያያዘውን resveratrol የተሰኘ ንጥረ ነገር ይዟል፡፡ በርካታ ጥናቶች በየዕለቱ አንድ ብርጭቆ ቀይ ወይን መጠጣት ለልብ ጥሩ እንደሆነ ቢገልፁም ኦቾሎኒ ግን ከወይን የበለጠ የresveratrol መጠን ይዟል፡፡
Peanuts
1. በማዕድናት የበለፀገ ነው
በፑርዱ ዩኒቨርሲቲ ተመራማሪዎች የተደረገ ጥናት 28 ግራም (1 አውንስ) ኦቾሎኒ ወይም የኦቾሎኒ ቅቤ (Peanut butter) በየዕለቱ ከተመገብን የማግኒዚየም፣ ፋይበርን፣ ኮፐር፣ ቫይታሚን ኢ እና arginine የተሰኙት ንጥረ ነገሮች መጠን ይጨምራል፡፡ እነዚህ ሁሉ የልብ በሽታን ለመከላከል ይጠቅማሉ፡፡ በዚህ ዩኒቨርሲቲ የተካሄደው ጥናት የኦቾሎኒ ሌላ ጠቀሜታንም አሳይቷል፡፡ ኦቾሎኒ ረሃብን በማስታገስም ከፍተኛ ጠቀሜታ አለው፡፡ በቅርብ ያገኙት ምግብ ኦቾሎኒን ብቻ ከሆነ ይመገቡት፡፡ ረሃብዎን ለሁለት ሰዓት ተኩል ያህል ያስታግስልዎታል፡፡ ከ20-30 ደቂቃ በላይ ከማይዘልቁት ኬኮች እና ሌሎች ስናኮች ጋር ስናነፃፅረው ኦቾሎኒን የሚደርስበት የለም፡፡

2. ኦቾሎኒ እና ካንሰር
በፍሎሪዳ ዩኒቨርሲቲ የተደረገ ጥናት ኦቾሎኒ በበሽታ ተከላካዮች የበለፀገ ነው ብሏል፡፡ ይህም ለልብ እና ለካንሰር በሽታዎች የሚያጋልጡንን ፍሪ ራዲካልስ ለመከላከል ያስችለናል፡፡ ከእነዚህ በሽታ ተከላካዮች ውስጥ P-coumaric acid የተሰኘው ኦቾሎኒው ሲቆላ የመከላከል ብቃቱ በ22% ይጨምራል፡፡

3. ስኳር በሽታን በኦቾሎኒ
ኦቾሎኒ የኮሌስትሮልን መጠንን ዝቅ በማድረጉ ረገድ የተመሰከረለት ከመሆኑም በላይ type 2 በተሰነው የስኳር ህመም ለተጠቁ ሰዎችም ይጠቅማል፡፡ ምግብ ከተመገቡ በኋላ የኢንሱሊን መጠን መጨመር የሚያጋጥም ሲሆን ኦቾሎኒ ይህን ችግር ያረጋጋል፡፡

4. መውለድን ያበረታታል
ኦቾሎኒ የሴቶችን ጤናማ ልጅ የመውለድ ዕድልን የሚጨምረውን folate የተባለ ንጥረ ነገር በጥሩ መጠን ይዟል፡፡ በዘርፉ በተደረጋጋሚ የተካሄዱ ጥናቶች በየእለቱ 400 ማይክሮግራም የፎሊክ አሲድ እንክብል በእርግዝና ወራት የሚወስዱ እናቶች በልጆቻቸው ላይ ሊያጋጥሙ የሚችሉ የጤና እክሎችን በ70% ለመቀነስ ያስችላል፡፡

5. የደም የስኳር መጠንን ያረጋጋል
ከሩብ ኩባያ ኦቾሎኒ ሰውነታችን ከሚያስፈልገው ማንጋኒዝ 35% ያህሉን እናገኛለን፡፡ ይህ ሚኒራል ስብ እና ካርቦሃይድሬትን ይቀንሳል፡፡ ሰውነታችን ካርቦሃይድሬትስን እንዲያዋህድ ይረዳል፤ የደም የስኳር መጠንን ያስተካክላል፡፡

6. የሐሞት ጠጠርን ይከላከላል
ኦቾሎኒ የሀሞት ጠጠር እንዳይፈጠር ይከላከላል መባሉ ሊያስገርም ቢችልም የተረጋገጠ እውነት ነው፡፡ ላለፉት 20 ዓመታት የተካሄዱ ጥናቶች በሳምንት 28 ግራም (የ1.00 ብር ኦቾሎኒ) የሚመገቡ ሰዎች የሐሞት ጠጠር በሰውነታቸው ውስጥ የመፈጠር ዕድሉ በ25% ይቀንሳል ተብሏል፡፡

7. ድብርትን ይዋጋል
ኦቾሎኒ Typtophan የተባለው አሚኖ አሲድ ጥሩ መገኛ ነው፡፡ ይህ አሚኖ አሲድ ሴሮቶኒን የተባለው ቁልፍ የአንጎል ኬሚካል እንዳይዋዥቅ ያደርጋል፡፡ ድብርት ሲያጋጥም ወደ አንጎል ሴሎች የሚለቀቀው የሴሮቶኒን መጠን ይቀንሳል፡፡ Tryptophan የሴሮቶኒንን የፀረ ድብርት ተፅዕኖ እንዲጨምር የሚያደርገው በደም ውስጥ የሴሮቶኒን መጠን በማሳደግ ነው፡፡

8. የማስታወስ አቅምን ይጨምራል
ኦቾሎኒ አለነገር ‹‹የአዕምሮ ምግብ›› የሚለው ስም አልተሰጠውም፡፡ በውስጡ የያዘው ቫይታሚን ቢ 3 ወይም ናያሲን አዕምሯችን የተለመደ ተግባሩን በብቃት እንዲወጣና የማስታወስ አቅማችን እንዲጨምር የማድረግ ብቃት አለው፡፡

9. በልብ በሽታ የመጠቃት ዕድልን ይቀንሳል
በርካታ ጥናቶች ኦቾሎኒን በቋሚነት መመገብ በልብ በሽ የመጠቃት ዕድልን እንደሚቀንስ ገልፀዋል፡፡ ኦቾሎኒ ለልብ ተስማሚ በሆኑ ሚኖአንሳቹሬትድ ፋትስ እና በሽ ተከላካዮች የበለፀገ ነው፡፡ በሳምንት ቢያንስ አራት ቀን ያህል ኦቾሎኒ ይመገቡ፤ በልብ የደም ስር በሽታዎች እና በሌሎችም የልብ ህመሞች የመጠቃት አጋጣሚዎችን በእጅጉ ይቀንሳሉ፡፡

10. ከእርጅና ጋር ተያይዞ የሚመጣ የመርሳት ህመምን ይከላከላል
ኦቾሎኒ አልዛይመርን የመሳሰሉ የመርሳት ህመሞችን በመከላከል ረገድ ያለውን ውጤት ለማወቅ በተደረገ ጥናት ላይ ከተሳተፉ ሰዎች ውስጥ ኦቾሎኒን በቋሚነት የሚወስዱት የመጠቃት ዕድላቸው በ70% ቀንሶ ተገኝቷል፡፡ የጥናቱ ውጤትም በየዕለቱ ሩብ ኩባያ ኦቾሎኒ መመገብ በቂ ናያሲን ለማግኘት ይረዳል ብሏል፡፡

11. ክብደት መጨመርን ይከላከላል
በቋሚነት ኦቾሎኒን መመገብ ክብደት እንዳይጨምር አስተዋፅኦ ያደርጋል፡፡ በጉዳዩ ላይ የተካሄደ ጥናት ቢያንስ በሳምንት ሁለት ጊዜ ኦቾሎኒ የሚመገቡ ሰዎች ምንም ከማይበሉት ጋር ሲነፃፀር ክብደት የመጨመር ዕድላቸው ቀንሶ ተገኝቷል፡፡

12.የጨው መጠኑ ዝቅተኛ ነው
ከፍተኛ የጨው (ሶዲየም) መጠን የደም ግፊት እንዲጨምር ያደርጋል፡፡ ኦቾሎኒ ዝቅተኛ የጨው መጠን አለው፡፡ ይህም ጤናማ ልብ እንዲኖረን ያደርጋል፡፡

ጥብቅ ማሳሰቢያ
ኦቾሎኒ ምንም አይነት አስገራሚ ፈውስና የጤና ጠቀሜታ ቢኖረውም እርስዎ ግን አለርጂክ ከሆኑ አንዲትም ፍሬ መብላት አይኖርብዎትም፡፡ በአብዛኛው በኦቾሎኒ የሚነሳ አለርጂ እስከ ሞት የሚያደርስ ጉዳት ያስከትላል፡፡ ኦቾሎኒን አዘውትረው ለመመገብ ከመወሰንዎ በፊት ሐኪምዎን ያማክሩ፡፡

ናሚቢያ፤ ሌላዋ የፍትሕ ጀግና! ኢትዮጵያስ? –ኪዳኔ ዓለማየሁ

$
0
0

“ዘ ጋርዲያን” (The Guardian) በተሰኘው ታዋቂ ጋዜጣ እ.አ.አ ነሐሴ 15 ቀን 2006 እንደ ተዘገበው፤ የጀርመን መንግሥትን በመወከል፤ ወ/ሮ ሔይደማሪ ዊዞረክ-ዜዩል (Mrs. Heidemarie Wieczorek-Zeul)፤ የጀርመን የልማት ሚኒስትር፤ ሐገራቸው እ.አ.አ. በ1904 በናሚቢያ ነዋሪዎች (ሔሬሮዎች) ላይ ስለ ፈጸመችው የዘር ማጥፋት ወንጀል ይቅርታ ጠይቀዋል። ለዚህም ወንጀል፤ ናሚቢያውያን (ሔሬሮዎች) ከይቅርታ መጠየቁ በተጨማሪ $4 ቢሊዮን ካሣ እንዲከፈል የጀርመን መንግሥትን መጠየቃቸው ተገልጿል። ከዚህ ቀጥሎ በቀረበው ምንጭ ላይ በመጠቆም ዝርዝር ሐተታውን መመልከት ይቻላል፤

http://www.theguardian.com/world/2004/aug/16/germany.andrewmeldrum

ከላይ በተጠቀሰው ዜና እንደ ተገለጸው፤ ጀርመኖች በፈጸሙት ወንጀል 65 000 ሔሬሮዎች (በኋላ ናሚቢያን) እንደ ተጨፈጨፉ ታውቋል። በጊዜው የነበረው የጀርመኑ የጦር መሪ፤ ጀኔራል ሎታር ቮን ትሮዛ፤ የናሚቢያን ጎሳ (ሔሬሮዎችን) ጥርግርግ አድርገው እንዲጨርሱ ትእዛዝ ማስተላለፉ ተገልጿል። የዚህ የጀርመን ጄኔራልና “የኢትዮጵያ ጨፍጫፊ” በመባል የሚታወቀው የሮዶልፎ ግራዚያኒ አስተሳሰብና ተግባሮች ተመሳሳይነት የሚያስገርም ነው። ለማንኛውም፤ የናሚቢያ መንግሥትና ናሚቢያውያን በሐገራቸው ላይ ለተፈጸመው ወንጀል በመቆርቆር ፍትሕ እንዲገኝ በመታገል ላስገኙት የመጀመሪያ ተጨባጭ ውጤት ሊደነቁ ይገባል። ምንም እንኳ፤ ለጊዜው የጀርመን መንግሥት የሚፈለግበትን ካሣ ለመክፈል ፈቃደኛ ባይሆንም በናሚቢያ ሕዝብና መንግሥት በኩል በቀጣይ የሚከናወነው ጥረት ተገቢውን የፍትሕ ውጤት እንደሚያስገኝ ይታመናል። ለማስታወስ ያህል፤ ናሚቢያ፤ በኢትዮጵያ ድጋፍ ጭምር ከቅኝ ግዛት ቀምበር የተላቀቀችው በቅርብ ጊዜ መሆኑ የታወቀ ነው።

ከናሚቢያ በተጨማሪ፤ ተመሳሳይ የፍትሕ ጀግንነት ካስገኙት ሐገሮች ውስጥ፤ እሥራኤል፤ ሊቢያ፤ ኬንያና ኢንዶኔዚያ ይገኙበታል። ከነዚህ ውስጥ በተለይ እሥራኤል ይቅርታ በመጠየቋም ሆነ በተከፈላት እጅግ ከፍ ያለ ካሣ በኩል ተምሳሌት የሆነች ሐገር ናት። ሌላዋ ለሐገሯ ክብርና ፍትሕ በመቆም ተጨባጭ ውጤት ያስገኘች ሐገር ሊቢያ ናት። በነግራዚያኒ መሪነት ሊቢያ የኢጣልያ ቅኝ ግዛት በነበረችበት ጊዜ ለተፈጸመው የ30 000 ዜጎች ጭፍጨፋ ኢጣልያ ለሊቢያ $5 ቢሊዮን ለመክፈል መስማማቷ ተረጋግጧል። ኬንያም፤ በእንግሊዝ መንግሥት፤ እንዲሁም ኢንዶኔዚያ በኔዘርላንድስ መንግሥት በቅርቡ ይቅርታ ተጠይቀው ካሣ እንዲከፈላቸው ተደርጓል። እነሱም ለሐገራቸው ክብርና ፍትሕ ታግለው መብታቸውን በማስከበራቸው ሊደነቁ ይገባል።

ትልቁ ጉዳይ፤ ኢትዮጵያ ለደረሰባት እጅግ መራርና አሰቃቂ የፋሺሽት ኢጣልያ የጦር ወንጀል ምን ጥረት እየተከናወነ መሆኑን የሚያጠይቀው ነው። እንደሚታወቀው፤ እ.አ.አ. በ1935-41 ፋሺሽት ኢጣልያ ኢትዮጵያን በወረረችበት ዘመን፤ አንድ ሚልዮን ኢትዮጵያውያን ተሰውተዋል። ከነዚሁ ውስጥ፤ በሶስት ቀኖች ብቻ (የካቲት 12-14 ቀኖች 1929 ዓ/ም)፤ በአዲስ አበባ ከተማ፤ 30 000 ኢትዮጵያውያን ተጨፍጭፈዋል። በተጨማሪም፤ 2000 ቤተ ክርስቲያኖች፤ 525 000 ቤቶችና 14 ሚሊዮን እንስሶች ወድመዋል። እንዲሁም መጠነ-ሰፊ የሆነ የኢትዮጵያ ንብረት በፋሺሽቶች ተዘርፎ አሁንም በቫቲካንና በኢጣልያ መንግሥቶች ይዞታ የሚገኝ አለ።

በኢትዮጵያ ላይ፤ በመርዝ ጪስ በመጠቀም ጭምር፤ ለተፈጸመው የጦር ወንጀል፤ ኢጣልያ እስካሁን ድረስ የከፈለችው ኢምንት የሆነ፤ ቆቃ ግድብ የተሠራበት $25 ሚሊዮን ብቻ ነው። ኢንዲያውም፤ የጦር ወንጀሉ አልበቃ ብሏት፤ “በእንቅርት ላይ ጆሮ ደግፍ” እንደሚባለው፤ በቅርቡ፤ የኢጣልያ መንግሥት ለግፈኛው የጦር ወንጀለኛ ለግራዚያኒ ልዩ መታሰቢያና መናፈሻ አስመርቃለታለች። በነገራችን ላይ፤ በምረቃው ሥነሥርዓት ላይ የቫቲካን ተወካይ ተገኝተው እንደ ነበር ቢ.ቢ.ሲ ዘግቧል።

ባቲካንም በጊዜው የነበሩት ፖፕ ፓየስ 11ኛና የፋሺሽቱ መሪ፤ ሙሶሊኒ፤ እጅና ጓንት ሆነው በኢትዮጵያ ላይ ለተፈጸመው የጦር ወንጀል፤ እስካሁን ድረስ የኢትዮጵያን ሕዝብ ይቅርታ አልጠየቀችም። አይሑዶችን ግን፤ በናዚ ጀርመኒ ስለ ደረሰባቸው ጭፍጨፋ በጊዜው የተቃውሞ ድምፅ ባለማሰማቷ ብቻ በመደጋገም ይቅርታ ጠይቃለች።

በአጠቃላይ፤ ኢትዮጵያ ለተፈጸመባት የጦር ወንጀል የሚገባት ፍትሕ፤

1ኛ/ የኢጣልያ መንግሥት ለኢትዮጵያ ሕዝብ ተገቢውን ካሣ እንዲከፍል ማድረግ፤ ይኸውም መከናወን ያለበት

ለኢትዮጵያ ሕዝብ በተጨባጭና ለዘለቄታው በሚጠቅም መንገድ፤ ለምሳሌ አስፈላጊ በሆኑ ፕሮጀክቶች

ሊፈጸም ይገባል።

2ኛ/ ቫቲካን የኢትዮጵያን ሕዝብ ይቅርታ ልትጠይቅ ይገባል።

3ኛ/ ከኢትዮጵያ የተዘረፉት ንብረቶች ለባለቤቱ ለኢትዮጵያ ሕዝብ እንዲመለሱ ማድረግ ያስፈልጋል። አመላለሱ

ግን አስተማማኝ በሆነ መንገድ ለመጪው ትውልድ ሁሉ ታሪካዊ ማስረጃነቱ ተጠብቆ እንዲቆይ ማረጋገጥ

ያስፈልጋል።

4ኛ/ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት በኢትዮጵያ ላይ የተፈጸመውን ወንጀል መዝግቦ ተገቢው ፍትሕ እንዲገኝ

አስፈላጊውን እርምጃ መውሰድ ይገባዋል።

5ኛ/ ለግፈኛውና ወንጀለኛው ፋሺሽት፤ ለግራዚያኒ፤ አፊሌ ከተማ (ኢጣልያ) የተቋቋመው መታሰቢያና መናፈሻ

መወገድ ይገባዋል።

በተጨማሪ፤ ሰሞኑን የቫቲካን ከፍተኛ መልእክተኞች ቡድን ኢትዮጵያን በመጎብኘት ላይ በመሆኑ ከቫቲካን ስለሚያስፈልገው ፍትሕ ጉዳይ ለመነጋገር ጥሩ አጋጣሚ ሊያስገኝ ይችላል። የሚመለከታቸው የመንግሥት ባለሥልጣኖች፤ በተለይ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መሪዎችና ሌሎችም በኢትዮጵያ ለሐገር ፍትሕ የሚታገሉ ሰዎችና ድርጅቶች በዚህ አጋጣሚ ቢጠቀሙ መልካም ይሆናል።

ዓለም-አቀፍ ሕብረት ለፍትሕ – የኢትዮጵያ ጉዳይ (Global Alliance for Justice – The Ethiopian Cause) www.globalallianceforethiopia.org ከላይ ለተዘረዘሩት አምስት ዓላማዎች እየተንቀሳቀስ መሆኑንና በሚቀጥለውም የየካቲት 12 የሰማእታት ክብረ-በዓል ቀን፤ ከኢትዮጵያውያንና የኢትዮጵያ ወዳጆች ጋር በመተባበር በዓለም ዙሪያ ከ30 ከተሞች በላይ ለሐገር ፍትሕ ጥረቱን ይቀጥላል። በዚህ አጋጣሚም፤ ከዚህ በላይ በተጠቀሰው ድር-ገጽ ውስጥ የሚገኘውን ዓለም-አቀፍ አቤቱታ አንባቢዎች እንዲፈርሙት ይጋብዛል።

ውድ ሐገራችን የሚገባትን ክብርና ፍትሕ እንድትጎናጸፍ ኢትዮጵያውያን በሙሉ ተባብረን እንድንታገልና ተፈላጊውን ውጤት እንድናስገኝ ቸሩ የኢትዮጵያ አምላክ ይርዳን። አሜን።

 

Comment

 

 

 

አቶ ሽመልስ ከማል ከአቶ ሬድዋን ሁሴን ጋር በመጋጨታቸው አኩርፈው ቤት መቀመጣቸው ተሰማ

$
0
0

የመንግስት ኮምኒኬሽን ጽ/ቤት ሚኒስትር ዴኤታ የሆኑት አቶ ሽመልስ ከማል ከ ሚኒስትሩ ሬድዋን ሁሴን ጋር መግባባት ባለመቻላቸው አኩርፈው ቤት በመቀመጥ መደበኛ ሥራቸውን እያከናወኑ አለመሆኑን ምንጮች ገልጸዋል።

አቶ ሽመልስ ከደባል ሱስ ጋር በተያያዘ በመደበኛ የስራ ሰዓታቸው ሊገኙ ባለመቻላቸው ሚኒስትሩ ይህን ባህሪያቸውን እንዲያስተካክሉ ቢነግሩዋቸውም ሊያስተካክሉ ፈቃደኛ ባለመሆናቸው የተፈጠረ መሆኑን ምንጮች ይገልጻሉ።
shimelis kemal
የአቶ ሽመልስን ሃላፊነት ደርበው እየሰሩ ያሉት በቅርቡ ከዱር እንስሳት ጥበቃ ባለስልጣን ዳይሬክተርነት ተነስተው የመንግስት ኮምኒኬሽን ሚኒስትር ዴኤታ በመሆን የተሾሙት አቶ እውነቱ ብላታ ናቸው።

አቶ ሽመልስ በቅርቡ የታዩት የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት የቦርድ ሊቀመንበር በመሆናቸው በድርጅቱ ስብሰባ ላይ ብቻ ነው፡፡ የፕሬስ ድርጅት ስራ አስኪያጅ አቶ ሰብስቤ ከበደ ከአቅም ማነስና የመልካም አስተዳደር ችግር ጋር ተያይዞ በድርጅቱ ጋዜጠኞች እየቀረበባቸው ያለውን ግልጽ ትችትና ቅሬታ በተደጋጋሚ ስብሰባዎች ላይ በመገኘት ከማስተባበላቸውም በተጨማሪ ጥያቄውን የሚያነሱ ጋዜጠኞችን እስከማስፈራራት የደረሰ ንግግር ሲያደርጉ የተሰሙት አቶ ሽመልስ፣ መደበኛ ስራቸውን መተዋቸው በኮምኒኬሽን መ/ቤቱ የመነጋገሪያ አጀንዳ ሆኖአል፡፡

አቶ ሽመልስ ከማል በአቶ በረከት ስምኦን ደጋፊነት የብሮድካስት ባለስልጣን ዋና ስራአኪያጅ የነበሩ ሲሆን፣ የ97 ምርጫን ተከትሎ የቅንጅት አመራሮችና ጋዜጠኞች በተከሰሱ ወቅት አቃቤ ሕግን ወክለው ሐሰተኛ መረጃዎች እንዲቀርቡና ሐሰተኛ ምስክሮችን በገንዘብ በመግዛትና በመደለል ለኢህአዴግ ውለታ ለመስራት የጣሩ ሰው መሆናቸው ይታወቃል፡፡

ይሁን እንጅ አቶ በረከት ከጤና ጋር በተያያዘ ስራቸውን እየተዉ በመምጣታቸው አቶ ሽመልስ ብቸኛው ደጋፊያቸውን አጥተዋል። አቶ ሽመልስ አቶ በረከትን የመተካት ህልም ቢኖራቸውም ሳይሳካላቸው አቶ ሬድዋን ቦታውን እንዲወስዱ ተደርጓል። በሁለቱ ባለስልጣኖች መካከል ባለው ልዩነት የተነሳ፣ አቶ ሽመልስ ከስራቸው የሚባረሩበት ቀን እሩቅ ላይሆን እንደሚችል ወይም በገዛ ፈቃዳቸው ስራቸውን በመልቀቅ ከአገር ለመውጣት ሙከራ ሊያደርጉ እንደሚችሉ ጉዳዩን በቅርብ የሚከታተሉ ታዛቢዎች ይገልጻሉ። የአቶ ሽመልስ የስልጣን ቆይታ በከፍተኛ ህመም ከሚሰቃዩት ከአቶ በረከት ስምኦን ህልውና ጋር የተያያዘ መሆኑን ታዛቢዎች ይናገራሉ።

Source: ኢሳት ዜና

የአንድነቱን ጉባዔ በወፍ በረር (ዳንኤል ተፈራ)

$
0
0

እንደ መነሻ

ዳንኤል ተፈራ

ዳንኤል ተፈራ

ከሁለት ወር በፊት አንድነትን እንዲመሩ በጠቅላላ ጉባዔ የተመረጡት ኢ/ር ግዛቸው ሺፈራው ጥቅምት ሁለት ቀን 2007 ዓ.ም ካቢኔያቸውን በትነው ስልጣናቸውን በፈቃዳቸው ለብሔራዊ ምክር ቤቱ አስረከቡ፡፡ የቀድሞው ፕሬዘዳንት ኢ/ር ግዛቸው ለምክር ቤቱ ባሰሙት ንግግር በአመራራቸው ያልተደሰቱ በሀገር ውስጥና በውጭ የሚኖሩ የፓርቲው አባላትና ደጋፊዎችን የ‹‹ልቀቅ›› ጫና መቋቋም እንዳልቻሉና ከህሊናቸው ጋር ተማክረው ለፓርቲው ጥቅም ሲባል በፈቃዳቸው ሃላፊነታቸውን ለመልቀቅ እንደወሰኑ ተናገሩ፡፡

ምክርቤቱም በጥሞና አድምጧቸው ሲያበቃ ውሳኔያቸውን በአድናቆትና አክብሮት በመቀበል በክብር ሸኛቸው፡፡ በጉዳዩ ላይም ጊዜ ወስዶ መከረ፡፡ አንድነትን ያለመሪ ለአንድ ቀንም ቢሆን ማሳደር አደገኛ እንደሆነና የፕሬዘዳንት ምርጫውን ማከናወን እንደሚገባም ወሰነ፡፡ ይህንን ለመወሰን የሚያስችል ስልጣን እንዳለው ከደንቡ ተጠቀሰ፡፡ ‹‹ብሔራዊ ም/ቤቱ ደንብ ከማሻሻል ውጭ ጠቅላላ ጉባዔውን ወክሎ እንዲንቀሳቀስ ውክልና ተሰጥቶታል›› ይላል፡፡ በዚህ የጠቅላላ ጉባዔ ውክልናው መሰረት ሦስት ዕጩ ፕሬዘዳንቶችን በጠቅላላ ጉባዔው የማወዳደሪያ መስፈርት መሰረት አወዳድሮ አቶ በላይ ፈቃዱን የፓቲው ፕሬዘዳንት አደርጎ ሾመ፡፡ ካቢኔያቸውን በአስቸኳይ አዋቅረው ወደ ስራ እንዲገቡ መመሪያ አስተላለፈ፡፡

ትንሽዋ ግርግር

በዚህ ሂደትም ‹‹አልተደሰትንም፣ ኢ/ር ግዛቸው ለምን ሄደብን!›› ያሉ ጥቂት ግለሰቦች ምክር ቤቱ ባካሄደው ምርጫ አምነው ከተሳተፉ በኋላ ሌላ የጎንዮሽ እንቅስቃሴ ያዙ፡፡ ይሄ እንቅስቃሴያቸውም መኢቲቪ፣ ምርጫ ቦርድና በትርፍ ፈላጊ ሃይሎች መታጀብ ጀመረ፡፡ እውነት መጥራቷ ላይቀር መንሻፈፍ ጀመረች፡፡ መግለጫዎች ተዥጎደጎዱ፡፡ የገዥው ፓርቲ ቀኝ እጅ ኢቲቪም ታይቶ በማይታወቅ መልኩ በየቀኑ ከስድስት ጊዜ በላይ በማስተላለፍ ትንሽዋ ግርግር ህይወት እንዲኖራት ጣረ፡፡ ነገርግን እውነቱ እንደዚያ አልነበረምና ግርግርዋ የአንድ ሳምንት ከመሆን አልዘለለችም፡፡ አዲሱ አመራር በስራ በመጠመዱ እና ለጓዳ ወሬዎች ምላሽ ባለመስጠቱ የአባላትን ትኩረትና ድጋፍ ለማግኘት ቻለ፡፡ ግርግሯም ከምሱሩ እንከሸፈ ጥይት ቱሽሽሽሽ አለች፡፡

ምርጫ ቦርድ ግን ምክርቤቱ የመረጠውን አመራር ዕውቅና ለመንፈግ አንገራገረ፡፡ በተደረጉ የደብዳቤ ልውውጦችም ምርጫ ቦርድ ሁሉንም ነገር ተቀብሎ ሲያበቃ አንዲት ትንሽ ቀዳዳ አመጣ፡፡ እሷም፡- ‹‹የጠቅላላ ጉባዔተኛ ኮረም ቁጥር በደንቡ ይካተት›› የምትል ናት፡፡ በተፈለገ ጊዜ ለመምዘዝ የታሰበች ቀይ ካርድ ናት፡፡ ደንብ ሊያሻሽል የሚችለው ደግሞ ጠቅላላ ጉባዔው ነው፡፡ ወደ ተሟሟቀ ህዝባዊ ንቅናቄ ስንገባ ይችን ካርድ ለመጠቀም እንዳሰቡ ግልፅ ነው፡፡ ምርጫ ቦርድ በተወሰኑ ፓርቲዎች ላይ እንደሚያደርገው ጥብቅ ቁጥጥር 60 እና 70 በሚላቸው ፓርቲዎች ላይ ማድረግ ቢችል የፓርቲዎቻችን ቁጥር ከ5 ሊዘል እንደማይችል እርግጠኛ ነኝ፡፡ ስለዚህ አንድነት የምርጫ ቦርድን የመጫወቻ ካርድ ማስጣል እንደሚገባ አመነ፡፡ ጠቅላላ ጉባዔውን መጥራት ለእንደ አንድነት ያለ ሀገራቀፍ መዋቅር ላለው ፓርቲ ብዙ ከባድ አይደለም፡፡ ሆኖም አያውቅም፡፡ እንዴውም በዚህ ወቅት በመላ ሀገሪቱ ያሉ አመራሮችን ማግኘት በአንድ ድንጋይ ሁለት ወፍ ይሉት አይነት ነው፡፡

ጉባዔው

ጉባዔ ለማካሄድ ቀን ተቆረጠ፡፡ ያለችው አንድ ሳምንት ብቻ ነበረች፡፡ በሀገር ውስጥ ያለው አመራርና አባላት እንዲሁም በውጭ ያሉ ብርቱ ደጋፊዎቻችን ተረባረቡ፡፡ ለጠቅላላ ጉባዔ አባላት ጥሪ ተላለፈ፡፡ የዞንና የወረዳ አመራሮች ጉዳዩን በንቃት ይከታተሉት ነበርና ሆ ብለው አዲስ አበባ ገቡ፡፡ ህወሃት/ኢህአዴግን ያስደነገጠ ጉባዔ ነበር፡፡ በአንድ ሳምንት እንደዚህ የደመቀ ጉባዔ ማካሄድ ብር ለሚነሰንሰው ገዥ ፓርቲ እንጅ ለተቃዋሚዎች የሚቻል አይመስልም፡፡ ለዚህም ‹‹ጉባዔ ጥሩ!›› እንደማስፈራሪያ ያገለግላል፡፡ አንድነት ግን በሀገራቀፍ ደረጃ ያለውን አቅም አሳየ፡፡

አርብ በማለዳው ከ400 በላይ የሚሆነው የጠቅላላ ጉባዔ ተሳታፊ በኢትዮጵያችን ባንዲራ በተመሰለ አለባበስ አረንጓዴ፣ ቢጫና ቀይ ለብሶ አዳራሹን ሞልቶታል፡፡ ሁሉም ላይ እልህና ወኔ ይነበባል፡፡ ስብሰባው የተጠራበት አጀንዳ ለውይይት ክፍት ሆነ፡፡ ትንሽዋን ግርግር ለመፍጠር የሞከሩ ግለሰቦች ጉባዔተኛው ፊት እንዲከራከሩ ወይም ሂሳቸውን እንዲሰለቅጡ ጥሪ ቢደረግላቸውም ሳይመጡ ቀሩ፡፡ የተገኙ ግለሰቦችም እንደ አሮጌ ቴፕ እየተንተፋተፉ ለምን ወደ ኢቲቪ እንደሄዱ ለማቅረብ ቢሞክሩም ከውግዘት በስተቀር ምላሽ አጡ፡፡ ምክንያቱም ኢቲቪ ለተቃዋሚው ያለው ምልከታ ይታወቅ ነበርና አኮረፍን ብለው ወደ ኢቲቪ መሄዳቸው ክስረት ነበር፡፡

እነሆ ጠቅላላ ጉባዔው ምክር ቤቱ የወሰደው ርምጃ ጠቅላላ ጉባዔው በሰጠው ውክልና መሰረት በመሆኑ ደንባዊም ተገቢም ነው ሲል ወሰነ፡፡ በላይ ፈቃዱም ፓርቲውን እስከ ቀጣይ ጉባኤ ድረስ የፓርቲው ፕሬዘዳንት በመሆን እንዲመራ በማለት በከፍተኛ ድምፅ ወሰነ፡፡ የሚገርመው ከራሱ ከበላይ የቀረበውንና ሌሎች አመራሮች የደገፉትን ዕጩዎች ቀርበው ፕሬዘዳንት ይመረጥ የሚል ሃሳብ ጠቅላላ ጉባኤው ውድቅ በማድረግ የም/ቤቱ ውሳኔ ትክክል ነው በማለት በሙሉ ድምፅ መወሰኑ ነው፡፡

ይሄው ግዙፍ የአንድነት የፖለቲካ ሃይል ደንቡንም አሻሽሏል፡፡ ሌሎች የፖለቲካ ውሳኔዎችንም አሳልፏል፡፡ አንድነት በ2007 ዓ.ም ሀገራቀፍ ምርጫ አሸናፊ ሃይል ሆኖ እንዲወጣ በሚያስችሉት ጉዳዮች ላይ ጥናቶች ቀርበው ውይይት አድርጓል፡፡ ህዝቡን ያሳተፈ ህዝባዊ ንቅናቄ እንዲደረግ እና ምርጫውን ነፃና ፍትሃዊ ለማድረግ ትግሉ ተፋፍሞ እንዲቀጥል ከስምምነት ላይ ደርሷል፡፡

ተደራጅ፣ የምርጫ አስፈፃሚዎችን ተከታተል፤ አምባገነኖችን የምትቀጣበትን የምርጫ ካርድ ያዝ፤ ድምፅህ እንዳይዘረፍ ጠብቅ፤ ይህን ሁሉ አልፈው ከዘረፉህ በህዝባዊ እምቢተኝነት አምበርክካቸው የሚለውን ጉባዔተኛው በአንድ ድምፅ በመናገርና ቃልኪዳን በመግባት ታላቁ የአንድነት ጉባዔ በድል ተጠናቀቀ፡፡

2007 ለለውጥ!!

 

 

Hiber Radio: ኢትዮጵያና ግብጽ በአባይ ግድብ ጉዳይ የጀመሩትን ድርድር አቋረጡ፤ ኢራን ኤርትራ ላይ ወታደራዊ ቤዟ ማደረጓ ተቃውሞ ገጠመው

$
0
0
ጋዜጠኛ ሃብታሙ አሰፋ

ጋዜጠኛ ሃብታሙ አሰፋ

የህብር ሬዲዮ ታህሳስ 5 ቀን 2007 ፕሮግራም

< … የህወሃት ካንጋሮ ፍርድ ቤት የይስሙላ የመጨረሻ ውሳኔ ማለቁን ለአቶ ሀይለማሪያም ተነግሯቸው ይሆናል… ኮሚቴዎቹ ግን ቀድሞም ፖለቲካዊ ውሳኔ እንደሚሰጥ… የሙስሊሙ ተወካይ የሆኑትን ጀግኖቹን የመፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴዎች አስሮ በጎን ከሚመስሏቸው ጋር የሚደረግ ድርድር ግን… >

ጋዜጠኛ ሳዲቅ አህመድ ወቅታዊ ጉዳዮችን አስመልክቶ ከህብር ሬዲዮ ጋር ካደረገው ቃለ ምልልስ የተወሰደ (ሙሉውን ያዳምጡ)

<…አንድነት ሰሞኑን የሚያካሂደው ተደራጅ ሕዝባዊ ንቅናቄ ነው… የኢትዮጵያ ሕዝብ ተደራጅ ሕዝባዊ ንቅናቄ ሰፊ መሰረት ያለው ነው። ተደራጅቶ የምርጫ ካርድ መውሰድ አለበት ድምጹን እንዳይዘረፍ መጠበቅ አለበት አይን ባወጣ መልኩ ሲዘርፉት አትዘርፈኝም ብሎ መተናነቅ እምቢ ማለት መቻል አለበት …>

አቶ ዳንኤል ተፈራ የአንድነት የውጭ ጉዳይ ሀላፊ ፓርቲው ስለሚጀምረው ሕዝባዊ ንቅናቄ እና ተያያዥ ጉዳዮች ለህብር ከሰጡት ማብራሪያ የተወሰደ(ሙሉውን ያዳምጡት )

የአሜሪካ የስለላ ድርጅት(ሲ.አይ.ኤ) የጭካኔ ምርመራ(ቶርች) መፈጸም መጋለጥና ኢትዮጵያን ጨምሮ ተባባሪ አገራት ላይ የነበሩ እስር ቤቶች( ልዩ ዘገባ)

ሌሎችም

ዜናዎቻችን

ኢትዮጵያና ግብጽ በአባይ ግድብ ጉዳይ የጀመሩትን ድርድር አቋረጡ

የዘጠኙ ፓርቲዎች ትብብር አገዛዙ ከፍርሓት ተላቆ ለህዝብ ጥያቄ ምላሽ እንዲሰጥ ጠየቀ

ሁለተኛ ዙር የትግል መርሐ ግብር በቅርቡ እጀምራለሁ አለ

የቻይናው ኩባንያና ኢትዮ ቴሌኮም በሁለት መቶ ሚሊዮን ዶላር ክፍአ ተቃቃሩ

ቻይና ለህወሃት አገዛዝ የመከላከያ ሀይልና ለሚሊሺያ ማጠናከሪያ በሚሊዮን የሚቆጠር ድጋፍ ማድረጓ ተቃውሞ ገጠመው

በኢትዮጵያ ያለው ጭቆና በአገሪቱ ላይ የታለመውን ዕድገት እንደማያመጣ ተገለጸ

የቀድሞ የግብጽ ጄኔራል ኢራን ኤርትራ ላይ ወታደራዊ ቤዝ ማድረጉዋ ለአካባቢው ስጋት ነው ሲሉ አስጠነቀቁ

አንድነት ሕዝቡ አስቀድሞ ከተደራጀ ድምጹ ሲሰረቅ መከላከል ይችላል አለ

ለዘጠኙ ፓርቲዎች ሰልፍ ሲቀሰቅሱ በሽንት ቤት ታስረው የነበሩት በህመም ላይ ናቸው

ሌሎችም ዜናዎች አሉ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ የሰማያዊ ፓርቲ የፋይናንስ ጉዳይ ኃላፊ የሆኑትን አቶ ወሮታው ዋሴን ከስራ አባረረ

$
0
0

werotaw wassie
ከሁለት አመት በፊት በኢሜል ለህዳሴው ግድብ ገንዘብ እንዲያዋጡ በተጠየቁበት ወቅት ለተላከው የኢሜል መልዕክት አልከፍልም ብለው በመመለሳቸው ‹‹ሰራተኛ በማሳመጽ፣ የኢንዱስትሪ ሰላም በማናጋት›› በሚል ተከሰው ተባርረው በፍርድ ቤት ወደ ስራ መመለሳቸውን ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡አቶ ወሮታው ከስራ የተባረሩት ጥፋት ያጠፋን ሰራተኛ አልቀጣህም በሚል ሲሆን በእሳቸው ስር የነበረውና አጠፋ የተባለው ሰራተኛ ጉዳይ ተመርምሮ ወደ ስራ መመለሱ ታውቋል፡፡

አቶ ወሮታው ከእሳቸውም በላይ ጉዳዩ የሚያገባው የማኔጅመንት አባል በተመሳሳይ ጉዳይ የአምስት ቀን ደመወዝ ብቻ ሲቀጣ እሳቸው ከስራ መባረራቸው በፖለቲካ አመለካከታቸው ላይ የተመሰረተና ፖለቲካዊ ውሳኔ እንደሆነ ያሳያል ብለዋል፡፡ ከስራቸው ይሰራ የነበረው ሰራተኛ ጥፋተኛ አለመሆኑን የገለጹት አቶ ወሮታው ‹‹በፖለቲካ አመለካከቴ ምክንያት ሁልጊዜም እኔን ማባረር ይፈልጋሉ›› ሲሉ የተባረሩት በፖለቲካ አመለካከታቸው እንደሆነ ገልጸዋል፡፡
semayawi Party

አቶ ወሮታው ዋሴ ከሁለት አመት በፊት በኢሜል ለህዳሴው ግድብ ገንዘብ እንዲያዋጡ በተጠየቁበት ወቅት ለተላከው የኢሜል መልዕክት አልከፍልም ብለው በመመለሳቸው ‹‹ሰራተኛ በማሳመጽ፣ የኢንዱስትሪ ሰላም በማናጋት›› በሚል ተከሰው ተባርረው ከሁለት አመት በኋላ በፍርድ ቤት ወደ ስራ መመለሳቸውን ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡

በወቅቱ አየር መንገድ አቶ ወሮታው ዋሴ ካሳ ተከፍሏቸው እንዲለቁ ይግባኝ ጠይቆ የነበር ቢሆንም ፍርድ ቤቱ ጉዳዩን ለሁለት አመት ካራዘመ በኋላ ወደ ስራ እንዲመለሱ አዝዞ እንደነበር ገልጸዋል፡፡ ጥፋተኛ ነው ብሎ ያባረራቸው አየር መንገድ ወደ ስራ በተመለሱ በ15 ቀናት ውስጥ ሰርተውበት ወደማያውቁት ክፍል በማዘዋወር እድገት አግኝተው የማኔጅመንት አባል እንደሆኑ እንደገለጸላቸው የሚናገሩት አቶ ወሮታው እድገቱ ሰራተኛ ሲባረር የመክሰስ መብት ስላለው፣ በተቃራኒው ግን ሳይፈልጉት በእድገት የማኔጅመንት አባል እንዲሆኑ የተደረገው የማኔጅመንት አባል የሆነ ግለሰብ ቢባረርም የመክሰስ መብት የሌለው በመሆኑ ሆን ተብሎ ለማባረር የተደረገ ስልት ነው ብለዋል፡፡ አቶ ወሮታው በወቅቱ ይህን እድገት አልቀበልም ብለው እንደነበርም ገልጸውልናል፡፡
አቶ ወሮታው ዋሴ አሁን ከስራ ባባረራቸው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ውስጥ በተለያዩ የኃላፊነት ቦታዎች ላይ ለ14 ዓመታት ያህል ማገልገላቸውን ለማወቅ ተችሏል፡፡

ታላቅ መንፈሳዊ ጉባኤ ጥሪ ከሚኒሶታው ቅዱስ ዑራኤል ቤተክርስቲያን

$
0
0

ታላቅ መንፈሳዊ ጉባኤ ጥሪ ከሚኒሶታው ቅዱስ ዑራኤል ቤተክርስቲያን
gubael at Ourael_12_20_14


Sport: ደደቢት አሰልጣኙን አባረረ

$
0
0

Niguse Desta
ኢትዮ-ኪክ ኦፍ እንደዘገበው በ2007 የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ጅማሮው መልካም የነበረው የደደቢት ስፖርት ክለብ በተከታታይ ጨዋታዎች ካስተናገደው ተደጋጋሚ ሽነፈት በኃላ አሰልጣኙን አሰናብቷል።

ክለቡ እንዳስታወቀው በአሰልጣኝ ንጉሴ ደስታ የስራ ስንብት በሁለቱም አካላት ስምምነት እንደሆነ ቢገልፅም የቡድኑ በፕሪምየር ሊጉ የውጤት መንሸራተት በክለቡ ኃላፊዎች ዘንድ ክፉኛ ያሰቆጣ በመሆኑ በአሰልጣኙ መሰናበት ምክንያት ሆኗል። ክለቡ አዲሱን አሰልጣኝ በነገው እለት እንደሚያሳውቅ የተገኘው የክለቡ መረጃ ያመላክታል።

Health: የምትፈልጋትን ዓይነት የፍቅር አጋር እንዴት ማግኘት ትችላለህ? (ለወንዶች ብቻ)

$
0
0

True Love
ዕድሜዬ 28 ነው፡፡ በአንድ መንግሥታዊ ባልሆነ ግብረ ሰናይ ድርጅት ውስጥ ተቀጥሬ እሰራለሁ፡፡ ራሴን በሚገባ የማስተዳድር ሰው ነኝ፡፡ ቤተሰቤ ያን ያህል የእኔን እርዳታ ባይፈልጉም አልፎ አልፎ ግን አንዳንድ ነገር አደርግላቸዋለሁ፡፡ ትዳር በዓመትና በሁለት ዓመት ጊዜ ውስጥ የመመስረት ፍላጎት አለኝ፡፡ የምፈልጋትን አይነት የፍቅር አጋር ግን እስካሁን ድረስ አላገኘሁም፡፡

ከሁለት ሴቶች ጋር ከዚህ በፊት መቀራረብ የቻልኩ ቢሆንም አንዳቸውም ከወራት የዘለለ ዕድሜ ኖሯቸው ወደ ትዳር ማምራት አልቻሉም፡፡ አንዳንድ ጊዜ ‹‹ይኼ ነገር እኮ እንደው ምንም አልሳካ አለ፤ ችግር ይኖርብኝ ይሆን እንዴ?›› ብዬ አስባለሁ፤ ሌላ ጊዜ ደግሞ ‹‹ለነገሩ ያው ጊዜው ነው እውነተኛ አፍቃሪ እኮ አይገኝም፡፡ ሰው ማንነትን ሳይሆን ምን ምን አለው ብቻ ነው የሚለው፣ ሞልቶ ስላልተረፈኝ ይሆናል›› እላለሁ፡፡ አሁን አሁንማ እንደው አዳዲስ ሰው የመተዋወቅ ዕድሉም የለኝም፡፡ አንዳንዴ ለመተዋወቅ እሞክርና ያን ያህል እኔም ገፍቼ አልሄድም በእነሱ በኩልም የተለየ ፍላጎት አላይም፡፡ ሳልሰማ ወይ ህጉ ተቀይሮ ይሆን እንዴ? ብዬ ለራሴ ፈገግ እላለሁ፡፡ የምፈልጋትን አይነት የህይወት አጋር እንዴት ማግኘት የምችል ይመስላችኋል?›› 

ከምስጋና ጋር በረከት ነኝ፡፡

መልስ፡-

የሰው ልጅ በህይወቱ ዘመን ከሚያደርጋቸው ዋና ዋና ውሳኔዎች መካከል አንዱ የትዳር አጋር ምርጫ ማድረግ ነው፡፡ የትዳር አጋር ለማግኘት ወጥ ቀመር ባይኖርም ጠቃሚ የሆኑ አጠቃላይ መርሆዎች ይኖራሉ፡፡ እነዚህን መርሆዎች ከግንዛቤ ውስጥ በማስገባት ጥያቄህን ለመመለስ እሞክራለሁ፡፡

የአንተ ጥያቄ ‹‹የምፈልጋትን አይነት የህይወት አጋር እንዴት ማግኘት እችላለሁ?›› የሚል ስለሆነ ለዚህ ሊረዱህ የሚችሉ ሀሳቦችን ከዚህ በታች እገልፃለሁ፡፡

ለትዳር መድረስን ማረጋገጥ፡- የአንተ ዕድሜ 28 በመሆኑ ከዕድሜ አንፃር ከመድረስም አልፈሃል ማለት ይቻላል፡፡ ከዝቅተኛው የጋብቻ ዕድሜ አስር ዓመት ያህል ርቀሃል፡፡ መልካም የጋብቻ ወቅት የሚባለው 20ዎቹ አጋማሽ አካባቢ እንደሆነ ይታሰባል፡፡ ከዚህ አንፃር የአንተ ዕድሜ ለጋብቻ ከበቂ በላይ ነው፡፡ የኢኮኖሚ ነገር ሲታሰብ መንግሥታዊ ባልሆነ ድርጅት ውስጥ ትሰራለህ፤ ራስህን በሚገባ የምታስተዳድር ሰው ነህ፤ ወላጆችህም ቢሆኑ የአንተን እርዳታ የሚፈልጉ አይነት ሰዎች አይመስሉም፡፡ ስለዚህ በኢኮኖሚ በኩል ያለውንም ፈተና አልፈሃል፡፡ ከውስጣዊ ዝግጅት አንፃር ደግሞ ለማግባት ፍላጎት አለብ፡፡ አንዳንድ እርምጃዎችንም እየወሰድክ ትገኛለህ፡፡ ለጋብቻ መድረስህ ምንም ጥርጥር የለውም፡፡ አሁን ወደ ትዳር አጋር ፍለጋ እንሂድ!

መስፈርትን መቃኘት፡- ዋነኛው የአንተ ችግር እንደሆነ የተገለፀው የምትፈልጋትን አይነት የትዳር አጋር ማግኘቱ ላይ እንደሆነ ‹‹የምፈልጋትን አይነት የፍቅር አጋር ግን እስካሁን ድረስ አላገኘሁም›› የሚለው ሐሳብ ያሳያል፡፡ ለትዳር ዕጩ ከሚሆኑ ሴቶች መካከል አንዷን ለመምረጥ መስፈርት ያስፈልግሃል፡፡ በቅድሚያ አንተ የምትፈልጋትን የትዳር አጋር ምን አይነት ሴት እንደሆነች በትክክል እወቅ፡፡ መቼም የሆነ መስፈርት እንዳለህ አስባለሁ፡፡ ማንም ሰው የሚፈልገውን ሳያውቅ መምረጥ አይችልም፡፡ ምርጫ ካለ መስፈርት አለ ማለት ነው፡፡

የትዳር አጋር ተፈልጋ የማትገኘው በምርጫ መስፈርት ዝርዝር ብዛትና ደረጃ ችግር ሊሆን ይችላል፡፡ መስፈርቶችን ለትዳር አጋር ምርጫ ከመጠቀምህ በፊት በአንተ ለካቸው፤ አንተ መስፈርቶቹን ማለፍ ከቻልክ ጥሩ መስፈርት ነው ማለት ነው፡፡ ሌላም ሴት ማለፍ ትችላለች፡፡ አንተ በሁሉ ነገር ፍፁም እንዳልሆንክ፤ ፍፁም ሴትም የለችም፡፡

የትዳር ጓደኛ ምርጫ መስፈርቶችን በተመለከተ ጥቂት ጠቃሚ ሃሳቦችን ላንሳልህ፡፡ መልካም የትዳር አጋር ለማግኘት ከዚህ በታች የተጠቀሱ ነጥቦች ወሳኝ ናቸው፡፡

የዕድሜ መጣጣም፡- የሰው ውበት፣ ስሜት፣ አስተሳሰብ፣ እውቀትና ፍሬያማነት እንደ ዕድሜው የተለያየ ነው፡፡ በዕድሜ ከአንተ ጋር የምትጣጣም፣ አቻ የምትሆንህ ሴት ብታገኝ ይመረጣል፡፡ የአንተ ‹‹እናት›› ወይም ‹‹ልጅ›› የማትመስል እኩያህ የሆነች ሴት እርሷ ጥሩ የፍቅር ጓደኛ ትሆንሃለች፡፡ ሀብት፣ ንብረትና ሌሎች ጥቅሞችን ከእርሷ ወይም በእርሷ በኩል ለማግኘት ብለህ በዕድሜ የማትመጥንህን ሴት አትሞክር፡፡ በውጫዊ ውበት ተማርከህ ደግሞ በዕድሜ ከአንተ በጣም የምታንስ ሴትን መፈለግም ዞሮ ዞሮ በትዳር ውስጥ የፍቅር መጣጣም ችግርን ያስከትላል፡፡

የባህር/ሰብዕና መጣጣም፡- የፍቅር ጓደኛሞችን የትዳር ግንኙነት አስደሳችና ዘላቂ የሚያደርገው ዋናው የሁለቱ የባህሪይ መጣጣም ነው፡፡

የሰው ባህሪይ/ሰብዕና ከወጣትነት ዕድሜ በኋላ አንፃራዊ ቋሚነት አለው፡፡ ቁጡነት፣ ትዕግስተኝነት፣ አባካኝነት፣ ቆጣቢነት፣ ጠብ ጫሪነት፣ ዳተኛነትት ትጉነት፣ ተጠራጣሪነት፣ ታማኝነት… የሰብዕና መገለጫዎች ናቸው፡፡ ከአንተ ባህሪይ ጋር የሚሄድ ባህሪይ ያላትን ሴት መፈለግ ያስፈልግሃል፡፡ አንተም ሆንክ እርሷ ትክክለኛ ባህሪያችሁን በመጀመሪያ ግንኙነት ላትገልፁ ትችላላችሁ፡፡ ስለዚህ እንደ አስፈላጊነቱ ስፋትና ጥለቀት ያለው ጥናት ሊፈልግ ይችላል፡፡ የአንተም ሆነ የእርሷ ባህሪይ በቤተሰብ አካባቢ በሚገባ ስለሚታወቅ በጥበብ ከቤተሰብና ከጎረቤት ሰዎችና የትምህርትና የሰፈር ጓደኞች መረጃ መሰብሰብ ጠቃሚ ነው፡፡

የትምህርት ደረጃ፡- የሰው የመግባባት መጠኑ እንደ እውቀቱ ይለያያል፡፡ ተመጣጣኝ የትምህርት ደረጃ ያላቸው ጥንዶች እርስ በእርስ ለመግባባት የሚያስችላቸው እውቀት ይኖራቸዋል፡፡ የትምህርት ደረጃ እውቀትን መጨመር ብቻም ሳይሆን በማንነት ላይ ተፅዕኖ ስላለው ተመጣጣኝ ትምህርት ያላቸው ጥንዶች እርስ በርስ የመቀባበላቸው ዕድል የሰፋ ይሆናል፡፡ ስለዚህ ከአንተ ጋር በትምህርት ደረጃ ተመጣጣኝ የሆነች ወይም የምትቀርብ የትዳር አጋር ብታገኝ ይመረጣል፡፡

ባህል፡- እያንዳንዱ ሰው ያደገበት ባህል ውጤት ነው፡፡ በእያንዳንዱ ባህል ውስጥ መደበኛ ባልሆነ መንገድ የሚሰጥ ትምህርት አለ፡፡ ይህ ትምህርት የአንድን ሰው አስተሳሰብ፣ አመለካከት፣ የህይወት ዘይቤ፣ ቋንቋ፣ ሃይማኖት፣ አመለካከት፣ የህይወት ዘይቤ፣ ቋንቋ፣ ሃይማኖት፣ ሰብአዊ ግንኙነት፣ ይቀርፃል፡፡ አንተና የትዳር አጋር የምትሆንህ ሴት ያደረጋችሁት በተለያየ ባህል ውስጥ ከሆነ፣ ሁለታችሁም ከዚህ በላይ በተጠቀሱ ነገሮች ልትለያዩ ትችላላችሁ፡፡ ይህ ልዩነት ደግሞ በእናንተ ግንኙነት ላይ አሉታዊ ተፅኖ ያሳድራል፡፡ ስለዚህ በምርጫህ ሂደት ከባህል አንፃር ከአንተ ጋር የምትጣጣም ሴት ልጅ መምረጥ ሊመጣ የሚችለውን አሉታዊ ተፅዕኖ ለመቀነስ ይረዳሃል፡፡

የቤተሰብ ፈቃደኝነት፡- አንድ ጎልማሳ በህይወቱ ምርጫ ለማድረግ ሙሉ ሰው ነው፡፡ አንድ ሰው መልካምም ሆነ ክፉ ምርጫ በማድረግ በሚያጋጥመው ሁኔታ ቤተሰብ መሳተፉ አይቀርም፡፡ አንድ ሰው ከቤተሰቡ ጋር ያለው ግንኙነት በደም የተሳሰረ ስለሆነ ግንኙነቱ ጠንካራና ዘላቂነት አለው፡፡ በተለይ ማህበራዊ ትስስሩ ኃይለኛ በሆነበት እንደ ሀገራችን ባለ ማህበረሰብ ውስጥ ውሳኔዎችን ቤተሰብን አማክሮ ማድረግ ብልህነት ነው፡፡

በትዳር ጓደኛ ምርጫህ ቤተሰብህ ተገቢውን ምክርና ድጋፍ በመስጠት ከተሳተፉ በትዳር ጉዞህ ከአንተ ጋር ይሆናሉ፡፡ የእርሷ ቤተሰብ አንተን ከተቀበሉ እውነተኛ የቤተሰብ ቅልቅል ይፈጠራል፡፡ በሁለታችሁ አማካኝነት የሁለታችሁ ቤተሰብ ዘላቂ ወዳጅነትና ዝምድና ፈጠሩ ማለት ነው፡፡ የሁለታችሁ ወይም የአንዳችሁ ቤተሰብ ስምምነታችሁን አለመቀበል መጋባታችሁን ባይከለክልም በትዳር ጉዟችሁ ላይ መፍትሄ የሚፈልግ የቤት ሥራ ይሆንባችኋል፡፡

ፍቅር፡- የትዳር ግንኙነት ማሰሪያ ገመድ ፍቅር ነው፡፡ ትዳር በፍቅር ጀምሮ በፍቅር እንዲያልቅ የምታገባትን ሴት ከልብህ እንደምትወዳት እወቅ፡፡ ለትዳር ዕጩ ከሆኑ ሴቶች መካከል ዕድሜ ልክህን ከእርሷ ጋር ለማሳለፍ የተሰጠ ልብና የማያዳግም ውሳኔ ሊኖርህ ይገባል፡፡ ስለዚህ ከጊዜያዊ ስሜት ባለፈ ሁኔታ እርሷን በማንነቷ የሚቀበልና የሚንከባከብ ፍቅር ካለህ በትክክለኛ ጎዳና ላይ ነህ፡፡ ከልብህ የማትወዳት ከሆነ ግን በሁኔታዎች ግፊት እርሷን ማግባት የለብህም፡፡ ይህ በገዛ ፈቃድህ በራስህ ላይ መሸከም የማትችለውን የህይወት ዘመን ሸክም መጫን ነው፡፡

እንግዲህ መስፈርት ካለህ ከእነዚህ ሐሳቦች አንፃር እንደገና ቃኛቸው፡፡ ቅኝታቸውን ካስተካከልህ በኋላ ተጠቀም፤ እንደ አስፈላጊነቱም አንዳንዶቹን ማሻሻል ወይም መለወጥ ትችላለህ፡፡

ያልተሳኩ ሙከራዎችን መገምገም፡- የትዳር አጋር መፈለግ ሂደት ነው፡፡ በእያንዳንዱ እርምጃ እየተማርክበት የምትሄድ እንጂ በአንድ ጊዜ የሚሳካ ነገር ላይሆን ይችላል፡፡ ዋናው ነገር ከሂደቱ አለመሳካት መልካም ነገር ተምረህ ወደፊት የተሻላ ነገር ለማድረግ መሞከር ነው፡፡

አለመሳካትን ለትምህርት ከተጠቀምክበት የተሻለ ምርጫ ለማድረግ ዕድል ይኖርሃል፡፡ ነገር ግን አንተ የጀመርከው ነገር ለፍሬ አለመብቃቱ አንተ ስለራስህ እንድትጠራጠር ምክንያት ከሆነ ጉዳቱ የከፋ ይሆናል፡፡

የትዳር አጋር ምርጫ አለመሳካቱ ብቻ ሳይሆን በማንነትህና ስለሌሎች ባለህ እይታህ ላይ አሉታዊ ውጤት ያሳድራል፡፡ ከሁለት ጊዜ ሙከራ በኋላ በአንተ ህይወት እየሆነ ያለው ይህን ይመስላል፡፡ ማንነትህን መጠራጠር፣ ሴቶችን መኮነንና በሁኔታዎች ማሳበብ ቀስ በቀስ ራስህንም እንዳትቀበልና ከሰዎችም ጋር ተገቢውን ግንኙነት እንዳታደርግ ምክንያት እየሆነ ነው፡፡

ስለዚህ እስካሁን ድረስ የወሰድካቸው እርምጃዎች አንተ ወደምትፈልገው ውጤት ያላደረሱህ ለምን እንደሆነ ሚዛናዊ በሆነ ሁኔታ ገምግም፡፡ ማሻሻል የምትችላቸውን ነገሮች አስተካክልና ወደፊት ቀጥል፡፡

ትጋትን መጨመር፡- ከደብዳቤህ መንፈስ ትንሽ የትጋት ማነስ ያለብህ እንዲሁም ነገሮችን ቀለል አድርገህ የምትመለከት አይነት ሰው ትመስላለህ፡፡ የምትፈልጋትን አይነት የፍቅር ጓደኛ በእጅህ ለማስገባት ትጋት ያስፈልግሃል፡፡ የሴቶቹን ፍላጎትና የልብ መከፈት እያስተዋልክ የግንኙነት ጥልቀትህን ቀስ በቀስ እየጨመርክ መሄድ ይገባሃል፡፡ የተዋወካትን ሴት ልጅ በመልካም ሁኔታ በመያዝ ትውውቁን ወደ ግንኙነት ማሳደግ፣ ለአንተ ፍላጎት እንዲኖራት ራስህን በተገቢው መንገድ ማስተዋወቅ፣ እርሷንም ለማወቅ ጥረት ማድረግ፣ ቀጠሮ ወስዶ መገናኘት፣ ግንኙነቱን ማሳደግ፣ አለመግባባቶቹን በሰከነ መንገድ መፍታት፣… እያልክ ሂደቱን እስከ ግብ ድረስ መቀጠል አለብህ፡፡

መልካም የትዳር አጋር የምታገኘው በትጋት ከሰራህ ነው፡፡ በትጋት የሚሻና የሚፈልግ ሰው መልካም ሚስት ያገኛለ፡፡ ሴቶችም ከልቡ የሚፈልጋቸውን ሰው ማየት ይፈልጋሉ፡፡ ደጅ ማስጠናቱን ሁሉ ችሎ የሚከታተላቸውና ለእውነተኛ ፍቅርና ጓደኝነት የሚፈልጋቸው ሰው ያገኛቸዋል፡፡ በማያቋርጥ ትጋትና መሻት ውስጥ እውነተኛ ፍቅር መኖሩን የሚያመክት ፍንጭ እንዳለ ይታሰባል፡፡ ስለዚህ በሴቶቹ ፍላጎት አለማሳየታቸው ተከፍተህ አትሽሽ፡፡ ‹‹እምቢ›› ወይም ‹‹ችላ›› ማለታቸው የአንተን እውነተኛ ፍቅርና ፍላጎት ለመለካትም የሚጠቀሙበት መንገድ ሊሆን ይችላል፡፡ በእርግጥ የአንተ ኢላማም ከአቅም በላይ ከሆነ ተገቢ ባልሆነ ስፍራ ጊዜን ማጥፋት ይሆናል፡፡ ኢላማህን በልክህ አድርግ፣ እስክትመታም ትጋ፣ ተስፋ አትቁረጥ!

የግንኙነት አድማስን ማስፋት፡- እንደ ፈላጊ የምትፈልገውን ለማግኘት ያ የሚፈለገው ነገር ያለበት ቦታ መሄድ ያስፈልግሃል፡፡ ዓሳ ለማጥመድ ዓሳ የሚገኝበት ወንዝ ወይም ባህር መሄድ አለብህ፡፡ ዓሳ ወደ ቤት አይመጣልህም፡፡ ‹‹አሁን አሁን አዳዲስ ሰው የመተዋወቅ እድሉም የለኝም›› የሚለው ሐሳብ ለአንተ የትዳር አጋር ፍለጋ ጉዞ ትልቅ እንቅፋት ሊሆን ይችላል፡፡

ለመሆኑ ከአዳዲስ ሰዎች ጋር የመተዋወቅ ዕድል እንዳይኖርህ ያደረገው ነገር ምንድነው? አንተ የምትፈልጋት ሴት እቤት አትመጣልህም፡፡ እርሷ ልትገኝ የምትችልባቸው ስፍራዎች በመሄድ ትውውቅና ግንኙነት መመመስረት ይገባሃል፡፡ እነዚህ የትዳር ጓደኛ የምታገኝባቸው ስፍራዎች የተለያዩ ናቸው፡፡ ለምሳሌ የስራ ቦታ፣ ጎረቤት፣ የስብሰባ ቦታዎች፣ ገበያ ስፍራ፣ ተከራይተህ የምትኖርበት ግቢ ውስጥ፣ ትምህርት ቤት፣ አምልኮ ስፍራ፣ ታክሲ መጠበቂያ አካባቢ፣ ታክሲ ውስጥ፣ መዝናኛ ስፍራዎች፣ ምግብ የምትመገብበት ሆቴል፣ ወዘተ ናቸው፡፡

በተገቢ ጊዜ መሰሎችህ ያሉበት ስፍራ በመሄድ የፍቅር ጓደኛህን መፈለግ ጀምር/ቀጥል እንጂ ‹‹ከአዳዲስ ሰዎች ጋር የመተዋወቅ ዕድል የለኝም›› ብለህ ጊዜህን በከንቱ አታሳልፍ፡፡ ልብህ ከፈቀደ ከሰዎች ጋር የመተዋወቅ መንገድ አይጠፋም ብዬ አስባለሁ፡፡

በመጨረሻም መልካም የትዳር አጋር የሚያገኝ ሰው ቀድሞ ራሱን ያወቀ ሰው ነው፡፡ እውነተኛ አፍቃሪ ለማግኘት አንተ በቅድሚያ እውነተኛ አፍቃሪ መሆን አለብህ፡፡ ሴት ልጅ እውነተኛ ፍቅርን ከአንተ ካገኘች በተለይ በወጣትነት ጊዜ ‹‹ምንም›› አትፈልግም፡፡ እውነተኛ ፍቅር ከሀብትና ከሌሎች ጥቅሞች ይልቅ ሴት ልጅን ወደ ግንኙነት የመሳብ ኃይል አለው፡፡ ስለዚህ ከልብህ አፍቅር፤ የልብ አፍቃሪ ታገኛለህ!

ቴዲ አፍሮ በድጋሚ ለማክሰኞ ጠዋት ተቀጠረ (ተጨማሪ አዳዲስ መረጃዎች ከዘ-ሐበሻ ምንጮች ይዘናል)

$
0
0

ዘ-ሐበሻ ታዋቂው ድምፃዊ ቴዲ አፍሮ ከሃገር እንዳይወጣ ከኤርፖርት ከተከለከለበት ጊዜ አንስቶ የተለያዩ መረጃዎችን እያቀረበችላችሁ ትገኛለች:: በየዕለቱ ከአንባቢዎቻችን የሚደርሱን “የቴዲ ጉዳይ ምን ላይ ደረሰ?” “ምን አዲስ ነገር አለ?” ጥያቄዎችም በርካታ ናቸው:: በዚህም መሠረት ለውድ አንባቢዎቻችን ለጉዳዩ ቅርበት እንዲኖራችሁ አዳዲስ ነገሮችን ከምንጮቻችን አሰባስበናል::
Teddy afro
የዘ-ሐበሻ የደህነንት ምንጮች እንደሚሉት ቴዲ አፍሮ ከሃገር እንዳይወጣ ፓስፖርቱን ያስቀማው ጉዳይ ከ11 ዓመት በፊት በአምስተርዳም ስለባንዲራ የዘፈነው ዘፈን ሰሞኑን ቴዲን ለመጉዳት ያሰቡ ሰዎች ከተቀመጠበት አውጥተው ዘፈኑን በሶሻል ሚዲያዎች ከለቀቁት በኋላ የስርዓቱን ሰዎች ስላናደዳቸው ነው:: ይህን ዘፈን ከ11 ዓመት በኋላ ማን ለቀቀው? የሚለው ጉዳይ እጅግ አነጋጋሪ ሲሆን ዘፈኑ ይበልጥ የነበረው በቴዲ ቅርብ ሰው እጅ ሰው ብቻ ስለነበር ሰውዪው ይህን ማድረግ የፈለገው ለበቀል እንደሆነ ብዙዎች ይጠረጥራሉ:: ይህ የቴዲ የቅርብ ሰው የነበረው ከድምፃዊው ጋር በአሁኑ ወቅት የማይሰራና የተለያየ በመሆኑ በንዴት ቴዲን እጎዳለሁ በሚል ከ11 ዓመት በፊት የተሠራን ሙዚቃ አዲስ በማስመሰል ለቆታል:: ይህ ሙዚቃም የሕወሓት/ኢሕ አዴግን አመራሮች በጣም አናዷቸዋል – እንደ ዘ-ሐበሻ የደህንነት ምንጮች::

ምንጮች እንደሚሉትና ዘ-ሐበሻ ባለፈው አርብ እንደዘገበችው ቴዲ ከፍርድ ቤት ከሃገር ቤት እንዳይወጣ የተሰጠ እግድ እንደሌለ የሚገልጽ ደብዳቤ ያወጣ ሲሆን ፓስፖርቱን የያዙበት ደህንነቶች ለዛሬ ሰኞ እንደሚሰጡት ቀጥረውት የነበረ ቢሆንም ዛሬም እንደተለመደው ሳይሰጠው ቀርቷል:: እንደለመዱትም ደህንነቶቹ ለነገ ማክሰኞ ቀጥረውታል:: ደህነንቶቹ ቴዲን በየጊዜው በማመላለስ ለማስቃየትና ለማማረር ቆርጠው እንደተነሱ የሚናገሩት የዘ-ሐበሻ ምንጮች በማን እንደታዘዙ የታወቀ ነገር አለመኖሩ ሃገሪቷን ከቤተመንግስት ሳይሆን ከቤቱ ቁጭ ብሎ የሚመራት ማን እንደሆነ ለብዙዎች እንቆቅልሽ ሆኗል::

በተለይ ሰሞኑን በቴዲ ይህ ጉዳይ ከደረሰ በኋላ በኢትዮጵያ መንግስት አለ ብለው በትንሹም ቢሆን እምነት የነበራቸው ሰዎች በህግ የሚመራ መንግስት አለ የሚል እምነታቸው ተሟጦ እንዳለቀ በተለያዩ ማህበራዊ ሚዲያዎች ሲገልጹ ሰንብተዋል::

ወደ ተጨማሪ መረጃዎች ስንመጣ ቴዲ ከዛሬ ነገ አውሮፓ ይመጣል ብለው የሚጠባበቁት የባንዱ አባላት በሆላንድ አምስተርዳም የሚገኙ ሲሆን ድምጻዊው የፊታችን ቅዳሜ በኖርዌይ ኮንሰርት እንደሚኖረው ፕሮግራም የተዘርጋ ቢሆንም የቴዲ ፓስፖርት ከአዲስ አበባ ካልተመለሰለት ወደ ኖርዌይ እንደማይንቀሳቀሱ ታውቋል:: ከባንዱ አካባቢ እንዳገኘነው መረጃም ቴዲ በትክክል ነገ ማክሰኞ ፓስፖርቱ የማይሰጠው ከሆነ በአውሮፓ ሊደረጉ ቀጠሮ የተያዘባቸው ሁሉም ኮንሰርቶች ይሰረዛሉ; የባንዱ አባላትም ወደአሜሪካ ይመለሳሉ ተብሏል::

ዘ-ሐበሻ ከዚህ ቀደም ብላ እንደዘገበችው ቴዲ በፊላንድ እና በሆላንድ ሊያደርጋቸው የነበሩት ኮንሰርቶች በፓስፖርቱ መቀማት የተነሳ ተሰርዘዋል::

ተጨማሪ መረጃዎች እንደተገኙ ዘ-ሐበሻ ለአንባቢዎቿ ለማካፈል ዝግጁ ነች::

ሕዝባዊ ዕንቢተኝነት ለኢትዮጵያ ትንሳኤ!

$
0
0

ነብዩ ኃይሉ

ባሳለፍነው ሳምንት ቅዳሜ ህዳር 27 ቀን 2007 ዓ.ም ዘጠኝ ፓርቲዎች ያቋቋሙት ትብብር የጠራው የአዳር የተቃውሞ ሰልፍ፣ በገዢው ቡድን ውንብድና ከተስተጓጎለ በኋላ ስለሰላማዊ ትግል አይረቤነት የተለያዩ አስተያየቶች በመሰጠት ላይ ናቸው፡፡ የተወኑት አስተያየቶች “ትግሉ አልጋ በአልጋ መሆን አለበት” ከሚል የዋህ ልቡና የመነጩ የተስፋ መቁረጥ ስሜቶች ቢሆኑም፤ ጥቂት የማይባሉት ግን የህብረተሰቡን ቀልብ ከሰላማዊ ትግል አውድ ለማፋለስ ታቅደው የሚሰነዘሩ ይመስላሉ፡፡
Tensaye
በመሰረተ-ሀሳብ ደረጃ የትኛውንም የአገዛዝ ስርዓት ለመጣል የሚደረግ ትግል በአንድ ወጥ ቀኖናዊ የትግል ስልት ላይ ብቻ መመስረት ይገባዋል የሚል ድምዳሜ መስጠት አይቻልም፡፡ ሆኖም ከኢትዮጵያ ነባራዊ ሁኔታ አንፃር የትኛው የትግል ስልት ያዋጣል የሚለውን በኃላፊነት ስሜት የመምረጡ ተግባር ለታጋዩ የሚሰጥ ነው፡፡ በየትኛውም መለኪያ በትግል ላይ የሚፈጠር እንቅፋት ሁሉ ስልቱን ጥያቄ ምልክት ውስጥ ሊከት ግን አይችልም፡፡

ዓለም-አቀፍ ተሞክሮዎች እንደሚያሳዩት የአገዛዝ ስርዓት የሚወገድባቸው በርካታ መንገዶች አሉ፡፡ከሚያስከፍሉት መስዋዕትነት አንፃርም በደረጃ ማስቀመጥ ይቻላል፡፡ የመጀመሪያው የትጥቅ ትግል ነው፡፡ የትጥቅ ትግል መጠነ-ሰፊ ሰብአዊና ቁሳዊ ውድመት የሚያስከትል ከመሆኑም በላይ ዴሞክራሲያዊ ስርዓት ለማንበር እጅግ ፈታኝ ነው፡፡ በሰላማዊ ትግል ላይ የረጅም አመታት ጥናት ያደረጉትና በቅርቡ “ሰላማዊ ትግል 101” በሚል ርዕስ መጽሀፋቸውን ያሳተሙት አቶ ግርማ ሞገስ፣ የኢትዮጵያ ታሪክ ከጦርነት ጋር የተጋመደ መሆኑን ያስረዳሉ፡፡ “ሀገራችን በስልጣኔ እንዳትገሰግስ ደንቃራ የሆነባት አገዛዞችን በጦር ሀይል ለማስወገድ የሚደረጉ የእርስ በርስ ጦርነቶች ናቸው” ሲሉም ይሞግታሉ፡፡

“ለዘጠኝ መቶ አመታት ላላነሰ ጊዜ ኢትዮጵያ በዘመናዊ (Secular) ትምህርት፤ ትምህርቱን ተከትሎ ለሚመጣ ዘመናዊነት እና ስልጣኔ ጀርባዋን መስጠቷ ለኋላ መቅረቷ አንዱ አውራ ምክንያት እንደነበር ከላይ ለመግለፅ ተሞክሯል፡ ፡በእንቅርት ላይ ጆሮ ደግፍ እንዲሉ ደግሞ ቢያንስ ቢያንስ ከአክሱም ስልጣኔ መውደቅ በኋላ አምባገነኑ ህወሓት/ ኢህአዴግ በ1983 ዓ.ም ስልጣን እስከጨበጠበት 1983 ዓ.ም ድረስ የእርስ በርስ ጦርነት (ትጥቅ ትግል) አካሂዶ ስልጣን መያዝ ጀግና የሚያሰኝ ባህል ነበር/ነው፡፡ ነፍጥንና ጉልበትን መሰረት ያደረገው የመንግስት ሽግግር ባህሏ ኢትዮጵያን እጅ እና እግሯን ተብትቦ ስለስልጣኔ የምታስብበት መተንፈሻ ጊዜ እንኳን እንዳይኖራት
አድርጓት
ሞገስ፡ ትግል101”
ነበር።
ግርማ “ሰላማዊ 2006፡33-34

ሌላው የትጥቅ ትግል ደካማ ጐን፣ ትግሉ በሶስተኛ ወገን ጣልቃ-ገብነት ጭምር የሚወሰን መሆኑ ነው፡ ፡ በዘመናዊው የኢትዮጵያ ታሪክ እንደተመለከትነው ከሀገራችን ጋር መሠረታዊ የጥቅም ባላንጣነት ያላቸው ጐረቤት ሀገራት ለደፈጣ ተዋጊዎች ድጋፍ እንደሚሰጡ ተመልክተናል፡፡ አገራቱ የደፈጣ ተዋጊዎቹን የሚረዱት ኢትዮጵያን ከአገዛዝ ስርዓት ለማላቀቅ ሳይሆን፣ አማፅያኑ የመንግስትነት መንበር ሲይዙ የመንግስታቸውን ጥቅም ማስከበር ነው፡፡

ሌላው የአገዛዝ ስርዓቶች የሚወገዱበት መንገድ መፈንቅለ-መንግስት ነው፡ ፡ መፈንቅለ መንግስት፣ የጥቂት ባለስልጣናትና የጦር መሪዎችን ለስልጣን ከማብቃት ባለፈ ህዝብን የስልጣን ባለቤት በማድረግ አገዛዝን ሲያስወግድ አይታይም፡፡ በብዙ የአፍሪካ ሀገራት ሲተገበር እንዳስተዋልነውም፤ መፈንቅለ መንግስት የእርስ በርስ ጦርነት ምክንያት ነው፡፡ በቅርቡ ነፃነቷን ያገኘችው ደቡብ ሱዳን አሁን ያለችበትን ምስቅልቅል መመልከቱ የመፈንቅ ለመንግስትን አደገኝነት የሚያመላክት ነው፡፡ በውጤቱም ሆነ በሂደቱ አምባገነንን በሌላ አምባገነን ከመተካት አንፃርም ከትጥቅ ትግል የተለየ አይደለም፡፡ የበርካታ ሀገራት ዜጐች የስልጣናቸው ባለቤት የሆኑት ከላይ በተጠቀሱት ሁለት መንገዶች ሳይሆን በሀይል አልባ ህዝባዊ እንቢተኝነት ነው፡፡

የህዝባዊ እንቢተኝነት የትግል ስልት፣ ከክርስቶስ ልደት በፊት በጥንታዊያኑ ግሪክና ቻይና እንደተተገበረ የዘገቡ የታሪክ ድርሳናት ቢኖሩም፣ በይበልጥ ያስተዋወቀው ግን ህንዳዊው የነፃነት ታጋይ ማህተማ ጋንዲ ነው፡ ፡ የጋንዲ የህዝባዊ እንቢተኝነት አስተምህሮ፣ በሂንዱ ቋንቋ Sanskrit ahimṣṣ በመባል ይታወቃል፤ አስተምህሮው በትግል ሂደት ውስጥ በራስም ሆነ በሌሎች ላይ በየትኛውም ሁኔታ ጉዳት እንዳይደርስ የሚያስችል ነው፡፡ የትግል ስልቱ ሰላማዊነት የሚንፀባረቀው ሞራላዊ፣ ሀይማኖታዊና መንፈሳዊ ዕሴቶችን የያዘና አንድን ውጤት ለማምጣት በሰው፣ በእንስሳትም ሆነ በተፈጥሮ አካባቢ ላይ የሚያደርስ መሆን እንደሌለበት ያስተምራል፡፡ ህዝባዊ እንቢተኝነት ሀይል አልባ መሆኑም የአገዛዝ ስርአትን ለማስወገድ የሚከፈለውን መስዋዕትነት ውሱን ያደርገዋል፡፡ ህዝባዊ እንቢተኝነት በጥናትና በዕቅድ የሚከወን ነው፡፡ ባልተቀናጀና ግብታዊ በሆነ መንገድ የሚደረግ የተቃውሞ እንቅስቃሴ ግን ህዝብን ሽንፈት ከማለማመድ ባለፈ ህዝባዊ እንቢተኝነትን ይወልዳል ብሎ መጠበቅ አላዋቂት ነው፡፡

ያልተጠኑ፣ በግብታዊነትና በተናጥል የሚደረጉ ያልተሳኩ የተቃውሞ ትዕይንቶች በህዝቡ ውስጥ ሽንፈትን የሚጠሩ ናቸው፡፡ ህዝባዊ እንቢተኝነት፣ ከአነስተኛ የተቃውሞ ትዕይንት ወደ “ምድር አንቀጥቅጥ” የተቃውሞ ትዕይንትነት የሚያድግ እንደመሆኑ መጠን ከጅምሩ የሚደረጉ ተቃውሞዎች የተጠኑና ታቅደው የሚደረጉ መሆን ይገባቸዋል፡፡ ለራስ የሚሰጡ የተጋነኑ ወይም የተንኳሰሱ ግምቶችም ሆነ ለተቀናቃኝ የሚሰጡ የተጋነኑ አሊያም የተንኳሰሱ ግምቶች የሚፈጠሩት ጥናትና እቅድ ላይ የተመሰረቱ እንቅስቃሴዎች ባለመደረጋቸው ሳቢያ ነው፡፡ ባሳለፍናቸው ጥቂት አመታት እንኳን የተደረጉ የተቃውሞ ትዕይንቶችን ብንፈትሽ፣ የምናገኘው ውጤት አብዛኞቹ በተጠና እና በታቀደ ሁናቴ የተከወኑ እንዳልሆኑ እንረዳለን፡፡ ማንኛውም ተግባር አመቺ ጊዜ ይፈልጋል፤ ጥሩ የሚባል ጥናት የተሰራለትን አንድን ተግባር ውጤታማ እንቅስቃሴዎች ውሱኑንት ታይቶባቸዋል፡ ፡ የተቃውሞ እንቅስቃሴዎቹ ውጤትን ሊያመጡ እንዲችሉ ተደርገው ያተጠኑና አመቺ ጊዜ ተመርጦላቸው ያልታቀዱ በመሆናቸው ግብታዊነት የሚስተዋልባቸው ሆነዋል፡፡

ሌላው ሊነቀፍ የሚገባውና ህዝቡን ሽንፈት የሚያለማምደው የተቃውሞ እንቅስቃሴዎቹ የተናጠል መሆናቸው ነው፡፡ ህዝባዊ እንቢተኝነትን ያመጡ፣ በሂደትም ለውጥን ያበሰሩ እንቅስቃሴዎች ሁሉ የህዝቡን ትኩረት ያገኙት፣ ሁሉንም ህዝብ በአንድ የጋራ ተተኳሪ ነጥብ ላይ ያሰባሰቡ በመሆናቸው ነው፡፡ በሀገራችን የተደረጉና እየተደረጉ ያሉት የተቃውሞ እንቅስቃሴዎች ግን የህዝቡን የለውጥ ፍላጐት እውን እንዲሆን፣ ወደአንድ የትኩረት ነጥብ የሚስቡ ለመሆን አልቻሉም፡፡ ለዚህ ደግሞ ዋነኛው ምክንያት የተናጠል የተቃውሞ እንቅስቃሴዎች መኖራቸው ዋነኛው ምክንያት ነው፡፡ ተቃዋሚ ፓርቲዎችም ሆኑ ይፋዊ ያልሆኑት የቡድን መብት አራማጅ ስብስቦች፤ እንቅስቃሴያቸውን ወደአንድ የትኩረት ነጥብ እንዲወስዱ ይጠበቅባቸዋል፡፡ይህ መደረጉ በተቃውሞ ትዕይንቶቹ ላይ የሚገኘውን ተሳታፊ ቁጥር ከፍ እንዲል የሚያደርግ በመሆኑ፣ አገዛዙን የሚያንበረክክ ይሆናል፡፡ በየትኛውም መለኪያ ተፅዕኖ ከቁጥር ጋር ያለውን ትስስር ማስቀረት ስለማይቻል፣ የተናጥል እንቅስቃሴዎችን ማሰባሰብ የግድ አስፈላጊ ነው፡፡

ከላይ የተጠቀሱት ግዙፍ ውሱንነቶች፣ የነፃነት ትግሉን እጅ ከወርች ያሰሩ ከመሆናቸውም በላይ በህዝቡ ውስጥ የሽንፈት ስሜትን የሚዘሩ ናቸው፡፡ በተቃውሞ ትዕይንቶች ላይ የሚታየው አነስተኛ የሰው ቁጥር ለውጥን ሊያመጣ የሚችል የሀይል ሚዛን ተቃዋሚዎች ጋር እንዳለ ዋስትና ስለማይሰጥ፤ ህዝቡን ለተስፋ መቁረጥ አሳልፎ እንደሚሰጥ የሚያጠራጥር አይደለም፡፡

የያዝነው አመት ምርጫ የሚካሄድበት እንደመሆኑ ዘጠኙ ፓርቲዎች ምርጫው ፍትሀዊ እንዲሆን በመጠየቅ ሊያካሂዱት የነበረውን ሰላማዊ የተቃውሞ ሰልፍ፣ ጭካኔን በቀላቀለ ሁኔታ እንዲደናቀፍ መደረጉ ገዢው ቡድን ለሰላማዊ የስልጣን ሽግግር አሁንም አለመዘጋጀቱን የሚያሳይ ነው፡፡ ይህን በዕብሪት የተወጠረ፣ በመሳሪያውና በሰራዊቱ ብዛት የሚመካ ቡድንን ለማስወገድ ተመጣጣኝ አቅም መገንባት የግድ ይላል፡፡ ገዢው ቡድን የያዘው መሳሪያና የሰራዊት ብዛት ከኢትዮጵያ ህዝብ አቅም ጋር ሊወዳደር አይችልም፤ ይህን የግብፅ፣ የቱኒዝያ፣ የዩክሬንና ሌሎች በህዝባዊ ዕምቢተኝነት ግብአተ-መሬታቸው የተፈፀሙ አንባገነኖች ታሪክ ይመሰክራል፡፡

አንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ የኢትዮጵያን ህዝብ የስልጣን ባለቤት አደርጋለሁ አለ (VOA)

$
0
0

አንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ የሚልዮኖች ድምጽ ለነጻና ፍትሀዊ ምርጫ ባለው ዘመቻ የኢትዮጵያን ህዝብ የስልጣን ባለቤት አደርጋለሁ አለ። ፓርቲው በአሁኑ ጊዜ በመላ የሀገሪቱ ክፍሎች መዋቅሩን መዘርጋቱናን በየትኛውም ደረጃ የምክር ቤት እጩዎችን ለማቅረብ እንደሚችል ገልጿል።

አንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ በሚቀጥሉት የምርጫ ወራት በሚልዮኖች ድምጽ ለነጻና ፍትሀዊ ምርጫ የኢትዮጵያ ህዝብ የስልጣን ባለቤት እንዲሆን እናደርጋለን ሲል ዛሬ ረፋዱ ላይ በጽህፈት ቤቱ በሰጠው መግለጫ ላይ ባሰራጨው ጽሁፍ ግልጽ አድርጓል።

የአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ (አንድነት)
አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤ የአቋም መግለጫ
=======================================
ከዚህ ቀደም ፓርቲው ያካሄዳቸውን የሚልዮኖች ድምጽ ለነጻነትና የሚልዮኖች ድምጽ ለመሬት ባለቤትነት ንቅናቄዎች አስታውሶ በተለይ በመጀመርያው እንቅስቃሴ የፈለገውን ውጤት እንዳገኘ የፓርቲው የውጭ ግንኙነት ሃላፊ አቶ ዳንኤል ተፈራ አብራርተዋል።

ሶስተኛውና የመጨረሻው የአንድነቶች የሚልዮኖች ድምጽ እንቅስቃሴ ይኸው የሚልዮኖች ድምጽ ለነጻነትና ለፍትሀዊ ምርጫ የሚል መሆኑንም የጽሁፉ መግለጫ ይጠቁማል።

አንድነት በሰላማዊ መንገድ የስልጣን ሽግግር ለማምጣት ላቀደው ዋነኛ የትግል ምዕራፍ በሀገራችን እውነተኛ ለውጥ እንዲመጣ የሚፈልጉ ዜጎች ሁሉ ፓርቲውን በአበላነትና በደጋፊነት በመቀላቀል የለውጡ አካል እንዲሆኑ የሚያደርግ ተደራጅ 2007 ለለውጥ የሚል ሰፊ የማደረጀትና የቅስቀሳ ዘመቻ ለማካሄድ ዝግጅቱን እንዳጠናቀቀ ገልጿል። ሙሉውን ዘገባ ያድምጡ።

ፓርቲያችን አንድነት በኢትዮጵያ ፖለቲካ ውስጥ ሠላማዊ የሥልጣን ሽግግር እንዲኖር ለማድረግ በሠላማዊ ትግል ትንቅንቅ ውስጥ ካሉ ፓርቲዎች ግንባር ቀደሙ ነው!
በትግሉ ውስጥ ከፍተኛ ዋጋ በመክፈል ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ልዕልና እየተጋ ያለው ፓርቲያችን በየጊዜው በሚገጥሙት መሠናክሎች ከመዳከም ይልቅ እየጠነከረ፤ ውስጣዊ ዴሞክራሲው ከጊዜ ወደ ጊዜ እያጎለበተ የመጣ እንዲሁም የኢትዮጵያን ሕዝብ ጥያቄ በአስተማማኝ መንገድ ለመመለስ በሀገር አቀፍ ደረጃ ቁርጠኛ አባላትን ያፈራ በመሆኑ ኩራታችን ከፍ ያለ ነው፡፡
አንድነት በ2ዐዐ7 ዓ.ም. በሚካሄደው ምርጫ አሸናፊ ኃይል ሆኖ ለመውጣት መሠረተ ሠፊ እንቅስቃሴዎችን እያደረገ ይገኛል፡፡ በዚህ ሠፊ እንቅስቃሴያችን ምክንያትም ገዢው ፓርቲ በአባላትና አመራሮቻችን ላይ ከፍተኛ የሆነ የእስር፣ የማሳደድና የማጥፋት ሥራ እየሰራ ቢሆንም ፓርቲያችን ይህንን ሁሉ ጫና በመቋቋም አሁንም በሠላማዊ ትግል የኢትዮጵያን ሕዝብ የሥልጣን ባለቤት ለማድረግ በቁርጠኝነት ቆሟል፡፡
ለዚህ ቁርጠኝነታችንና ፓርቲያችን ስላለው መሠረተ ሠፊ አደረጃጀት ከዚህ አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤ በላይ ምስክር የለም፡፡ በአንድ ሳምንት ውስጥ ደረጃውን የጠበቀ ጉባኤ ለማድረግ ችለናል፡፡ ይሄ ፓርቲያችን የደረሰበትን እድገት የሚጠቁም ብቻ ሳይሆን ለሌሎች ፓርቲዎችም አርአያ ለመሆን የሚበቃ ነው፡፡
እኛ የእዚህ አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤ አባላትም በዛሬው እለት ባደረግነው አስቸኳይ ስብሰባም የሚከተሉትን ውሳኔዎች አሳልፈናል፡፡
1. የፓርቲው ብ/ም/ቤት የቀድሞው የፓርቲው ፕሬዚደንት ኢ/ር ግዛቸው ሽፈራው ስልጣናቸውን በፈቃዳቸው መልቀቃቸውን ተከትሎ ብ/ም/ቤቱ ባለው የጠቅላላ ጉባኤ ውክልና መሠረት ያካሄደው ፕሬዚደንታዊ ምርጫ ተገቢና ሕገ-ደንባዊ መሆኑን አረጋግጦ አቶ በላይ ፍቃዱን እስከሚቀጥለው የፓርቲው ጠቅላላ ጉባኤ የፓርቲው ፕሬዚደንት እንዲሆኑ በከፍተኛ ድምጽ ወስነናል፡፡
2. በመተዳደሪያ ደንቡ ውስጥ ከብ/ም/ቦርድ የሚፈለጉ ማብራሪያዎችን እና ሃሳቦች ተከትሎ ጠቅላላ ጉባኤው የተወሰኑ ማሻሽያዎች አድርጓል፡፡
3. መድረክን በተመለተ በፓርቲያችን ላይ የጣለውን ሁለተኛ እገዳ ተከትሎ የፓርቲው ጠቅላላ ጉባኤ በወሰነው መሠረት ብ/ም/ቤቱ ከመድረክ እንዲወጣ የወሰነውን ውሳኔ ተገቢ ሆኖ ስላገኘው በከፍተኛ ድጋፍ አፀድቋል፡፡
4. ገዢው ፓርቲ ህገ መንግሥቱን በመጣስ በእየእስር ቤቱ ያጎራቸውን የዴሞክራሲ አርበኞች በአስቸኳይ እንዲፈታ ጉባኤው አጥብቆ ይጠይቃል፡፡
5. የዜጎችን በነፃ የመደራጀት ነፃ አመለካከታቸውን በአምባገነንነት በማፈን ያሰራቸውን የነፃነት አርበኞች ፖለቲከኞች ፣ ጋዜጠኞች፣ ብሎገሮች፣ የቤተ እምነት መሪዎች በአስቸኳይ እንዲፈቱ እየጠየቅን መንግሥት በሩን ለብሔራዊ ውይይት ክፍት እንዲያደርግ ጉባኤው ጥሪውን ያስተላልፋል፡፡
6. የተቀማነውን ነፃነታችንን በድምፃችን ለማስከበር ‹2ዐዐ7 ለለውጥ› የሚል የህዝባዊ ንቅናቄ ዘመቻ አንድነት በዛሬው እለት ጠቅላላ ጉባኤው አውጇል፡፡ ስለዚህ መላ የኢትዮጵያ ሕዝብ በምርጫው በንቃት በመሳተፍ በምርጫ ካርዱ ነፃነቱን እንዲያስከብር አንድነት ፓርቲ ጥሪውን ለመላው ኢትዮጵያ ሕዝብ በአክብሮት ያስተላልፋል፡፡
በምርጫው በንቃት በመሳተፍ ነፃነታችንን እናስከብር!
የአንድነት አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤ ታህሣሥ 3/2ዐዐ7 ዓ.ም
አዲስ አበባ

10698475_829409667117784_3680643737158512454_n

Viewing all 15006 articles
Browse latest View live