Quantcast
Channel: Ethiopian News | ዘ-ሐበሻ | Latest News Provider | News For All
Viewing all 15006 articles
Browse latest View live

Hiber Radio: መምህር ግርማ በስዊስ ፖሊሶች ታገዱ፤ “የኢሳያስ አፈወርቂ ወደ ግብጽ መሔድ ቅር አያሰኘንም”–ኃይለማርያም

$
0
0

ጋዜጠኛ ሃብታሙ አሰፋ

ጋዜጠኛ ሃብታሙ አሰፋ


የህብር ሬዲዮ መስከረም 4 ቀን 2007 ፕሮግራም
እንኳን ለአዲሱ ዓመት በሰላም አደረሳችሁ!

<...>>

ፕ/ር ጌታቸው ሀይሌ በቀን አቆጣጠራችን ላይ ለህብር ሬዲዮ ከሰጡት ቃለ ምልልስ ቃለ መጠይቅ የተወሰደ(ሙሉውን ያዳምጡት)

>

ወ/ት ሜሮን አሀዱ ሊትል ኢትዮጵያ ተብሎ እንዲሰየም ትልቅ አስተዋጽዎ ካደረጉት አንዱዋ የዘንድሮውን በዓል አስመልክታ ከሰጠችን ማብራሪያ

በቬጋስ የኢትዮጵያዊነት ቀን ለመጀመሪያ ጊዜ በአደባባይ ከልጅ እስከ አዋቂ ኢትዮጵአውያን በአንድ ላይ ታድመውበት ደምቆ ተከብሯል

ለኢትዮጵያዊነት ቀን የተደረጉት የእግር ኳስና የጠረጴዛ ቴኒስ ውድድሮች እንዲሁም የሩጫው ውድድር በሶስት ታዋቂ ኢትዮጵያውያንን ያስታወሰ ነው። የክቡር አቶ ይድነቃቸው ተሰማ መታሰቢያ፣የጋዜጠኛና ገጣሚ ሰለሞን ተሰማና በአበበ በቂላ ስም ነበር። በዓሉን አስመልክቶ ውይይት ከተሌአዩ እንግዶች ጋር

የስኮትላንድ ሕዝበ ውሳኔ ዋዜማና የእንግሊዝ ፖለቲካ (ልዩ ዘገባ)

ዜናዎቻችን

የኤርትራው ፕ/ት ኢሳያስ አፈወርቂ ወደ ግብጽ መሔድ ቅር አያሰኘንም ሲሉ አቶ ሀይለማርያም ተናገሩ

ኢትዮጵያዊው የፈውስ አባት መምህር ግርማ በስዊስ ፖሊሶች ታገዱ

የግንቦት ሰባት ሕዝባዊ ሀይል የፖለቲካ ሀላፊ ዘመኑ ካሴ በስዊዘርላንድ ለተደረገው ስብሰባ ንግግር አደረገ

በአገር ቤት በሚገኙ ተቃዋሚዎች ላይ የሚደረገው ጫና በአዲሱም ዓመት ቀጥሏል

የአኙዋክ ጭፍጨፋ ተፋራጆች የቀድሞ የክልሉ ፕ/ት ስርዓቱን ለመጣል እታገላለሁ ከማለታቸው በፊት ከዓለም አቀፉ የወንጀለኞች ፍ/ር ቤት ሊቀርቡ ይገባል አሉ

በምዕራባውያን የሚደገፈው የኢትዮጵያው አገዛዝ የዜጎችን መሬት እየነጠቀ ሰብዓዊ መብት ጥሰት እንደሚፈጽም የኬኒያው ኔሽን ዘገበ

ሌሎችም ዜናዎች አሉ


ከጠባቡ እስር ቤት ሰፊውን መርጠናል –ጋዜጠኛ መልካም ሰላም ሞላ

$
0
0

ጋዜጠኛ መልካም ሰላም ሞላ

ጋዜጠኛ መልካም ሰላም ሞላ

ጋዜጠኛ መልካም ሰላም ሞላ

..እነሆ በስደት ስሜት ውስጥ ሆነን፣ ከሃገር መውጣት ከሞት የመረረ ጽዋ እንደሆነ እያወቅነው፤ ህሊናችንን ሽጠን ለሆዳችን ማደር ቢያቅተን ፣ ከህዝብ በተሰበሰበ ብር ተንደላቀን የህዝብን እውነት ቀብረን ህዝብ ለእኛ ባደራ ያስረከበንን እምነት ረግጠን እያጭበረበርን እየዋሸን እየቀጠፍን እንድንኖር የቀረበውን ጥያቄ ንቀን፣ እንደአለቆቻቸው እንደገደል ማሚቶ በሉ የተባሉትን እያስተጋቡ ከህሊናቸው ተጣልተው እንደሚያድሩት “የቁጩ በጎች”፤ በጋዜጠኛ ስም ተሸፍነን በአንድ ወቅት አብረናቸው ከበላን እና ከጠጣን በማህበራዊ ህይወታችን ብዙ መልካም ነገሮችን አብረን ከተቋደስናቸው ሰዎች /ኧረ ባጋጣሚም ቢሆን አንድ ቤት ውስጥ ከ20 በላይ ሰዎች ሆነን ካደርን/ ከወያኔ መዶሻ ተርፈው ጥቂት መራመድ ከቻሉ እና የነገ የሃገር ተስፋ ይሆናሉ ተብለው የሚጠበቁትን ሰዎች ጀርባ እንድንሰልል፣ስማቸውን እንድናጠፋ እና ለነደፉት የመበታተን እቅድ ተባባሪ እንድሆን ስንጠይቅ በፍጹም! ብለን የቀረበልንን የጉቦ ማታለያ ቤት እና ገንዘብ ረግጠን፣ እኛ የጀግኖች ኢትዮጰያዊያን ልጆች እንጂ የባንዳ ውላጆች አለመሆናችን አስረድተን፤ በተጨማለቀ ስርአት ውስጥ ህዝብን ለማታለል ከሚገነቡ ጥቂት ህንጻዎች ይልቅ በየጉራንጉሩ የሚጠፋው የሰው ህይወት የሚረገጠው የዜጎች መብት የሚካሄደው ኢ-ሰብአዊ ጥሰት አይተን እንዳላየን ሰምተን እንዳልሰማን ከማለፍ የሚመጣብን መቀበል ይሻላል ብለን እሾህና አሜኬላ በበዛበት የኢትዮጵያ የፕሬስ ስርአት አመታት አስቆጥርን፡፡

በጥቂት የገዥው መደብ ባለስልጣናት የሚካሄደውን ምዝበራ እና ዝርፊያ እያወቁ ጸጥ ማለት ከአእምሯችን በላይ ቢሆንብን፤ ገንዘብ የኢትዮጵያን ህግ ሲገዛ፤ ጥቂት የገዥው መደብ አቀንቃኞች ተመችቷቸው አብዛኛውን ሲጨቁኑ በዲሞክራሲ ስም አምባገነንነት አስፍነው እንደፈለጋቸው ታሪክ እያበላሹ፤ በፌዴራሊዝም ስም በጎሳ እና በዘር ኢትዮጵያን ለመበታተን ቆርጠው መነሳታቸውን እኛ እወቅን እነርሱ እየዋሹ እድሚያቸውን ለማረዘም የሚያደርጉትን ሂደት ለማክሸፍ ህይወታችን አደጋ ላይ ጥለን፤ እንደአህያ በዱላ የሚያምነው ጭንቅታቸው ሌት ከቀን አንዴ ከቤታችን አንዴ ከቢሯችን አንዴ በስልካችን አንዴ በቤተሰባችንን …. እየመጡ ችለን ብዙ መንገድ ለመጓዝ ጥረናል፡፡

የኢትዮጵያን ህዝብ ብሶት ማሰማት ለሙያ መታመን ነው ብለን፤ በሙያችን በቆየንባቸው ጊዜያት ዛሬም ከጫካ አስተሳሰብ ያልተላቀቀው የደህንነቶች የጉልበት ማስፈራሪያና መደለያ ሳያሸንፈን ለሙያችን ተገዝተን የኢትዮጵያ ህዝብ የናፈቀውን እውነትን ፍለጋ፣ ሰላምን ፍለጋ፣ ፍትህን ፍለጋ፣ ከሞቀው ቤታችን፣ ከደመቀው መንደራችን፣ በስስት ከሚያዩን ቤተሰቦቻችን፣ ሌት ከቀን ስለኛ ከሚያስቡ እና ከሚጨነቁ ጓደኞቻችን ርቀን፤ የነበረንን ሜዳ ላይ በትነን የምንወዳትን ሃገራችንን ትተን ከሃገር ተሰደንም ቢሆን ፤በዓሉ ቢያልፍም አልዘገየንም እና እንኳን ለዘመን መለወጫ በዓል አደረሳችሁ አልን፤ ከዚሁ ከስደት መንደራችን ከሌባ እና ፖሊስ ሩጫ ባስተረፍናት ጊዜ ተጠቅመን፡፡ ኮካዎች ሲንጫጩ (በልቶ ዝም የለምና) እኛም እዚህ ሆነን ከመከራችን ባስተረፍነው ፈገግታችን ሂሂሂ አልንባቸው፡፡ የራሳቸውን ማንነት ክደው የሙት መንፈስ ቅዠት የማስጠበቅና የማስቀጠል ቋሚ ስራቸው ስለሆነ ከእነርሱ የሚጠበቅ ነውና “የመለስ ራእይ” እየተሳካ ስለሆነ ደስታቸውን እንዲያከብሩ ፈቀድንላቸው፤ ባንፈቅድም ፈቅደዋልና ሳቅንባቸው፡፡ እድሜ ለወያኔ በዚህ 23 አመት የተወለድን ልጆች ራሳችንን እንድንችል የሚያደርግ ስርአት ባይፈጠርልንም ቤተሰቦቻችን ከእኛ አልፎ ለሌላው የሚርፍ ስራ እንደሚሰሩ እና መሰደዳችን እንዳመማቸው ግልጽ ነው፡፡

በተለይ ልክ እንደማንኛውም ሰው ከሃገር ተሰደዱ የሚለውን ዜና አይሉት ሰቆቃ በአዲስ አመት መግቢያ በአውዳመት መዳረሻ ሲሰሙ በጳጉሜ ያሳለፍነው ጥቁር ሳምንት ለእነርሱ አዲስ አመት አዲስ ሰቆቃ ይዞ በአደይ አበባ ሳይፈካ እንደጨለመ 2007 እያሉ ቀን መቁጠር ጀመሩ፤ ጥቁራቸውን እንደለበሱ፤ በርቀት የብርሃን ፍንጣቂ ጮራ እየናፈቁ እንደልባቸው ሰላም ተመለሱ ብለው መልካም ምኞታቸውን ለመናገር እንኳን ሲቃ አንቋቸው ሳይተነፈሱ ሰማይ ሰማዩን እያዩ ከፈጣሪያቸው ጋር እያወሩ ቤተሰቦቻችን አስቧቸው፡፡ አብዛኞች ስደተኛ ጋዜጠኞች የወያኔ ትውልድ ስላልሆኑ አብዛኛውን የእድሜ ዘመናቸውን የኖሩለት ሙያ የከፈላቸውን “ዉለታ”፣ ንብረታቸውን ሜዳ ላይ በትነው ግማሹን በማይረባ ዋጋ በነጻ መስጠት ከማይተናነስ አውጥተው ጥለው፤ አይደለም በዓል ደርሶ እንዲሁም በአዘቦት መምጣታቸውን በጉጉት ከሚጠብቁት ልጆቻቸው በስስት ከሚያዩዋቸው ቤተሰባቸው ከሚያስተዳድሩዋቸው ቤተዘመዶቻቸው ተነጥለው ቢሰደዱም፤ ቅሉ አንድ ሁለቱ እዚህ ያለውን ሁኔታ እንዲሰልሉ በወያኔ ተልከው የመጡም አልጠፉም፡፡ ለነገሩ ይሄ አይገርምም፡፡ እንኳን ተሰደን፤ ሀገር ቤት በጋዜጠኛ ሽፋን፤ በጓደኛ ሽፋን፤ በጉርብትና ሽፋን ተደብቀው አብረውን እየበሉ አብረውን እየጠጡ ክፉ ደጉን እያሳለፉ አብረውን እየሰሩ የገዥው መንግስት ተላላኪ ሆነው እያንዳንዷን እንቅስቃሴያችንን የሚያቃጥሩ “ጓደኞቻችን” እያወቅን እንዳለወቅን ሆነን ብዙ ኮካዎችን ስቀን አልፈናቸዋል፡፡ ጥያቄው የነጻነት እንጂ የዳቦ ቢሆን ኖሮማ ከተሰደደው አብዛኛው ጋዜጠኛ ተንደላቆ ለመንግስት አሸርግዶ በኖረ ነበር፡፡

ጥያቄው ኢኮኖሚ ቢሆን ኖሮማ ገና ድሮ እባካችሁ አትጻፉብን ምን እንዳርግላችሁ የየት ሃገር ቪዛ እንምታላችሁ ስንባል ዘንጠን በመረጥነው ሃገር በሄድን ነበር፡፡ ምን እስክንከሰስ አስቆየን? ጥያቄው የህሊና ሆነ እንጂ የሆድ ቢሆን ኖሮማ ባመጡልን መደለያ ተጠቅመን ለኛም ለቤተሰቦቻችን ህይወት የሚቀይር ብር በተቀበልንና የኢትዮጵያን ህዝብ ሮሮ እንዳልሰማን ባለፍን፡፡ መንገዳችን ሃገር ለመልቀቅ ቢሆን ኖሮ አብዛኛው ጋዜጠኛ ፓስፖርት በእጁ ያስምጣል እንጂ በተከሰሰ ማግስት ስለፓስፖርት ማውጣት ባልተጨነቀ ነበር፡፡ ጥያቄው የፍትህ እና የነጻነት ሆነ እንጂ ቪዛ ማግኛ ቢሆን ኖሮማ የተደራጀ ኑሮ እና ቤተሰብ ሃገር ቤት ውስጥ ባልመሰረተ ነበር፤ ባሳለፍነው ጥቁር ሳምንት አንዳንዱን ሰው ታዘብነው ብዙውን አከበርነው፡፡ ኮካዎችን…. አይ እነርሱማ ኮካ ናቸው፡፡ እኔን የገረመኝ ግን የባለቀለሞች ነው ፤ የባለ ቀለም ምልክቶች አስተሳሰብ፡፡ ወያኔ ለራሱ እንኳን በቅጡ የማይገባውን ፖሊሲውን በሰዎች ላይ ለመጫን እንዴ በስብሰባ አንዴ በስልጠና አንዴ በአበል ብዙ ጊዜ በግድ ለማስረጽ ሌት ተቀን ሲለፋ አካኪ ዘራፍ ያልነው፤ “የመለስን ራእይ በማጣጣል” ተብለን ስንወነጀል የመለስ ራእይ የዮሃንስ ራእይ አይደለም ያለመቀበል መብት አለን ብለን ስንከራከር እኮ አቋማችንን እየገለጽን እንጂ የመቃወም ሱስ ኖሮብን አይደለም፡፡ ዛሬም እናንተ አንዳንድ የባለቀለም አባላቶች ለምን ተሰደዱ ብላችሁ የራሳችሁን አስተሳሰብ እኛ ጋር ለመጫን ማሰባችሁ ያስቃል፡፡ ሰው የሚኖረው በገባው ልክ ነው፡፡ እኛ አስበን እንጂ አስበውልን አንኖርም፡፡ (በተለይ አንቺ የ10 ቀን መታሰር “ጀግና” ያደረገሽ ባለቀለም ሳሞራ የኑስ ከ11ኛ ክፍል አቋርጦ የኢትዮጵያን መከላከያ ልምራ ብሎ “ታሪክ” አበላሸ፤ ታሪክ እንዳይደገም እስኪ እልፍ ….እልፍ በይ… ) ለነገሩ እናንተ ባለቀለሞች ኢትዮጵያ ውስጥ ከአንድ ጋዜጠኛ ውጭ ያለ አይመስላችሁም ፤ እርሱ እናንተ ያላችሁ ባይመስለውም፡፡

ቢሆንም በጥቂቶች ብዙሃንን አንፈርጅም “ለምጣዱ ስንል አይጧን ትተናል” እና አፉ ብለን አሁንም ተስፋ ጥለናል፡፡ ቅር ብሎንም መልካም ምኞታችን አንነፍግም እና እንኳን አደረሳችሁ ብለናል፡፡ እናም ከዚህ ሁሉ ሃተታ በኋላ ወደ ቀደመ ነገራችን ስንመለስ በመሰደዳችን ከማንም እና ከምንም በላይ ላዘናችሁ ፈጣሪ እንዲከተለን ለጸለያችሁ ቤተሰቦቻችን፣ ጓደኞቻችን፣ ሳትነግሩን ብላችሁ የተቀየማችሁን ወያኔ ራሳችንን እንዳናምን አድርጎን በስልክ ማውራት ባንደፍርም፣ ከሃገርም ውስጥም ሆነ ውጭ ሰምታችሁ ደንግጣችሁ መልእክት የላካችሁ፣ ተናዳችሁ እላፊ ስድብ ላወረዳችሁብን ባለቀለሞችና ኮካዎች ፣ ካላችሁበት እኛን ለመርዳት እየተንቀሳቀሳችሁ ላላችሁት በሙሉ ለሁላችሁም መጭው ዘመን የሰላም እና የእርቅ እንዲሆን ተመኘን፡፡ ከጠባቡ እስር ቤት ሰፊው ይሻላል ብለን መርጠናል እና ሃገራችንን ኢትዮጵያ እግዚአብሄር ሰላሙን ያምጣላት፡፡

በዋሽንግተን ዲሲ ኢትዮጵያዊውን ወጣት ገጭቶ በመግደል የተሰወረ/ች ግለሰብ እየተፈለገ/ች ነው

$
0
0

(ዘ-ሐበሻ) ኢትዮጵያዊው ወጣት በረከት አለሙ በመኪና ተገጭቶ ህይወቱ ካለፈ በኋላ በብዙዎች ዘንድ መነጋጋሪያ ሆኗል። የዲሲ ሜትሮ ፖሊስ ይህን ወጣት ገጭቶ የተሰወረውን ግለሰብ/ የተሰወረችውን/ እንዲጠቁም የስልክ ቁጥሮችን በትኗል።
bereket alemu
ትናንት እሁድ ጠዋት በጆርጂያ ጎዳን በመኪና በመገጨት መሞቱ የተነገረለት ወጣቱ በረከት ዓለሙ በሚኪና የገጨው ግለሰብ ያመለጠ ሲሆን ፖሊስ የገጨውን መኪና ለመለየት በአካባቢው ያሉትን ካሜራዎች እየተመለከተ እንደሆነ ለማወቅ ተችሏል። የ26 ዓመቱ ወጣት በጣም ተግባቢና ከሰው ጋር የሚኖር እንደነበር የሚናገሩት ወዳጆቹ አሟሟቱ በመላው ዓለም አነጋጋሪ እንደሆነ ዘ-ሐበሻ ለመረዳት ችላለች።

በአይሳኢታ፣ በዱብቲ፣ በአዋሽ፣ በአሚ ባራ፣ በገዋኔ፣ በአፍዴራ፣ በዶቢና ሚሌ የሚገኙ አፋሮች መሬታቸውን ተቀምተው በርሃብ እየተቆሉ ነው

$
0
0

አኩ ኢብን ከአፋር ለዘሐበሻ እንደዘገበው

የደርግ ስርዓት ወድቆ የኢህአዴግ መንግስት ሲመጣ ብዙ የአፋር መሬት ወደ ትግራይ ክልል እንዲመለስ ተደርጓል። በሰሜናዊው የአፋር ክልል በዳሉል ወረዳ ይተዳደሩ የነበሩ ብዙ የአፋር ህዝቦች በግዴታ በትግራይ ክልል ውስጥ እንዲተዳደሩ ተደርገዋል!
ለምሳሌ፦ ያህል፥ ታላክ፣ ጎደለ፣ ሰሄሎ እና ሰውነ ሲሆን ከዚህ በላይ ስማቸው በተጠቀሱት ቦታዎች ከኢህአዴግ ሰርዓት በፊት ከአጼዎች ዘመን ጀምሮ የአፋር መሬት እንደነበረ ይታወቃል። ታላክ እና ጎደለ እሰከ ሰሄሎ በደጅ አዝማች አህመድ ሲተዳደሩ ሰውነ ደግሞ በኦና ማሕሙድ ይተዳደር ነበር።
afar 1

afar 2
በዚህ አካባቢ የሚተዳደሩ የአፋር ህዝቦች እስካሁን ድረስ በቋንቋቸው የመማር ማስተማር እንዲሁም ባህላቸውን የማሳደግ የሰብዓዊ መብት ያላገኙ ሲሆን በሚኖሩበት የትግራይ ክልል እንኳን የአፋር ብሄረሰብ አይባሉም ኢህአዴግ ይኸው ቆምኩላችሁ መብታችሁን አስከበርኩላችሁ እያለ የአፋር ህዝብ ግን ገና ጭቆና ላይ መሆኑን ለመላው የኢትዮጵያ ወገኖቻችንና ለዴሞክራሲም ሆነ ለሰብዓዊ መብት የሚታገሉ የመብት ታጋዬች ሊያውቁልን ይገባል! ህዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ ደርግን ለመዋጋት ወደ ጫካ ሲገቡ ይሄ የአፋር ህዝብ ለትግራይ ህዝብ የቅርብ ጎረቤት ስለነበር ምግባቸውን አብስለው ለተጋዬች ከማቅረብ ጀምሮ ከጎናቸው የቆመ ህዝብ ቢሆንም ዛሬም ከጭቆና ልወጡ አልቻሉም።

ወድ የተከበረችሁ ወገኖቼ ሆይ ይሄን ስናገር ግን የቀረው የአፋር ህዝብ መብት ተክሮለታል ማለት አይደለም! በክልላችን በወያኔ ያልተወረረ የአፋር መሬት የለም። በአይሳኢታ፣ በዱብቲ፣ በአዋሽ ፣በአሚ ባራ፣ በገዋኔ ፣በአፍዴራ ፣በዶቢና ሚሌ የሚገኙ አፋሮች በአሁኑ ጊዜ ከመሬታቸው ተፈናቅለው በረሀብ እየተሰቃዩም ይገኛሉ።

የተንዳሆ የስኳር ፋብሪካ የተጀመረው በ2001 ዓ.ም ቢሆንም እሰከ ዛሬ የኢትዮጵያ ህዝብ ከስኳር ችግር አልወጣም። ፋብሪካው ሙሉ በሙሉ የሚቆጣጠሩት የህወሃት ባለ ስልጣናት ሲሆኑ አብዛኛቸው ከመከላኪያ ሰራዊት በጡረታ የወጡ መኮነኖች ናቸው! የአፋር ክልል መንግስትም ቢሆን ለስራቸው የሚሰጠውን ባጀት ወደ ውጭ ሀገር እየላኩ ማስቀመጥ ብቻ ነው!! ሌላው ቀርቶ በአፋር ክልል በሰላም ሲኖሩ የነበሩ የአማራና የኦሮሞ ብሄር ተወላጆችን በግዳጅ ከአፋር ክልል እያስወጡ ይገኛሉ። በዚህ አመት ብቻ ከ400 ሺ በላይ የትግራይ ተወላጆች በሰፈራ ፕሮግራም ወደ አፋር ክልል ገብተዋል!!

በመጨረሻም:- የአፋር ህዝብ ከኢትዮጵያ ነፃነት ታጋዮች ጋር ለሚደረገው ትግል ከዳር እስከ ዳር ዝግጁ መሆኑን በአፋር ወጣቶች ስም ላረጋግጥላችሁ እወዳለሁ። የአፋር ህዝብ ይህ የአንባገነን ስርዓት አብቅቶ የነፃነት ፀሃይ የምትወጣበት ቀን በጉጉት የሚጠብቅ ጭቁን ህዝብ ነው!

ነፃነት ለኢትዮጵያ

አረንጓዴ ኢኮኖሚና መለስን ምን አገናኛቸው?

$
0
0

ጌታቸው ሺፈራው

የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ከአካባቢ ጥበቃ ጋር የተጣጣመ የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ ጋር የተያያዘ ነው፡፡ ይህ የኢኮኖሚክስ መርህ በበርካታ ምሁራን የተነሳ ቢሆንም መንግስታት ለጊዜያዊ ጥቅማቸው ሲያምታቱት ይስተዋላል፡፡ በአብዛኛው አረንጓዴ ኢኮኖሚ ሲባል እንደ ጸሃይ ብርሃንና ባዮ ጋዝን እንዲሁም የአየር ንብረትን ለመከላከል የሚያስችሉ (ለምሳሌ በኤሌክትሪክ መኪናዎችን) ቴክኖሎጅ መጠቀም ያካትታል፡፡ የውሃ ንጽህናን መጠናከርና ብከላን ማስወገድ፤ የፍሳሽ አገልግሎትን በማዘመንና ቆሻሻን እንደገና በመጠቀም አካባቢን ከብክለት መከላከል የዢሁ ስልት አንድ አካል ነው፡፡ ደንን ማልማት፣ መሬትን ከመከላት መከላከልና የመሳሰሉትን ከባቢ አየርን ለመከላከል የሚያስችሉ ዘዴዎችን መጠቀም ላይ የሚያተኩር ፖሊሲም ከአረንጓዴ ኢኮኖሚ ጋር ሲያያዝ ይታያል፡፡
በእርግጥ ምሁራንም ቢሆን አረንጓዴ ኢኮኖሚ የሚለውን ትርጉም እንደ የራሳቸው የሚተሩሙት መሆኑን ተከትሎ እስካሁን ግልጽ ትርጉም እንዳልተሰጠው የሚናገሩት በርካቶች ናቸው፡፡ ከዚህም አለፍ ሲል አረንጓዴ ኢኮኖሚ የሚባል ነገር የለም ከሚሉት ጀምሮ ከአፈጻጸሙ፣ ለመጠቀሚያነት ብቻ የሚውል መሆኑ፣ በትርጉም ልዩነትና በመሳሰሉት ተቃውሞዎች ይገጥሙታል፡፡

  Meles Zenawi

Meles Zenawi


አረንጓዴ ኢኮኖሚ እንደ መለስ ራዕይ

ከአቶ መለስ ሞት በኋላ ኢህአዴግ አዲስ አባዜ የተጠናወተው ይመስላል፡፡ ሁሉም የአገሪቱ ኢኮኖሚያዊ፣ ፖለቲካዊና ማህበራዊ ስኬቶች በአቶ መለስ የተወጠኑ መሆናቸውን በተደጋጋሚ ሲያወራ ይደመጣል፡፡ ተቋማት፣ ምሁራንና ሰራተኞች የሌሉ ያህል አቶ መለስ የሁሉም የአገሪቱ ፖሊሲና ስትራቴጅዎች ቀያሽና የመጽሐፎች ሁሉ ደራሲ ተደርገዋል፡፡ ልማታዊ መንግስትና አብዮታዊ ዴሞክራሲ የተባሉት በውል ያልተተረጎሙ እና በመልካም ተሞክሮነት ከሌሎች የተለበጡ የስልጣን መወጣጫ መርሆች ሳይቀር አቶ መለስ የፈጠሯቸው ተደርገው እየተወሩ ነው፡፡ አብዮታዊ ዴሞክራሲም ሆነ ልማታዊ መንግስት አቶ መለስ ስልጣን ከመያዛቸው በፊት ሌሎች ስርዓቶች ተግባራዊ ያደረጓቸው ቢሆንም በኢህአዴግ መንደር ግን የአቶ መለስ ግኝቶች ተደርገው እየቀረቡ ነው፡፡

በቅርቡ ደግሞ ኢህአዴግ አቶ መለስ የአረንጓዴ ኢኮኖሚን መርህ ለዓለም አማራጭ ማቅረባቸውን እየነገረን ነው፡፡ አረንጓዴ ኢኮኖሚ ባዮ ጋዝና የጸሀይ ብርሃን መጠቀም፣ ቆሻሻን እንደገና መጠቀም፣ ደን እንክብካቤ፣ የአካባቢ ጥበቃ ጋር ምቹ የሆኑ ምርቶች (አረንጓዴ ምርቶች) ማምረትና የመሳሰሉትን የሚያጠቃልል በመሆኑ ስሙ ተሰጥቶትም ሆነ ሳይሰጠው በርካታ የዓለም አገራት አቶ መለስ ከመወለዳቸው በፊት ጀምሮ ተጠቅመውበታል፡፡ ለአብነት ያህል የጸሃይ ብርሃንን በታዳሽ ምንጭነት ለመጠቀም የሚያስችለው የመጀመሪያው የዘርፉ (የአረንጓዴ) ቴክኖሎጅ የተሰራው እ.ኤአ በ1883 ቻርለስ ፍሪት በተባለ ግለሰብ ነው፡፡ ምንም እንኳ ይህ ቴክኖሎጅ በተለይ ኤሌክትሪክ ማመንጨት የቻለው ዘግይቶ ቢሆንም ይህም ቢሆን አቶ መለስ ስልጣን ከመያዛቸው 6 አመት ቀድሞ እ.ኤ.አ በ1985 ነው፡፡ ምዕራባዊያን አገራት ይህን ታዳሽ ሀይል አቶ መለስ ምኒልክ ቤተ-መንግስት ከመግባታቸው በፊት ወደ ሀይል ቀይረው ተጠቅመውበታል፡፡ ኢትዮጵያ ውስጥ ሀሳቡ ከመነሳቱ በፊት የሰሜን አፍሪካ አገራትና ጎረቤታችን ኬንያን ጨምሮ በርካቶቹ አገራት ተጠቅመውበታል፡፡

ለአረንጓዴ ቴክኖሎጂ እንደ አንድ ግብዓት የሚጠቀሰው ኢታኖል ነው፡፡ የኢታኖል ሳይንሳዊ ቀመር የተገኘው እ.ኤ.አ በ1840 ዎቹ ነው፡፡ አሜሪካውያን ይህ የኢታኖል ሳይንሳዊ ቀመር ከወጣበት ጊዜ ጀምሮ ለመብራትነት ሲገለገሉበት ኖረዋል፡፡ እንግዲህ አቶ መለስ ከመወለዳቸው ከሁለት መቶ አመት በፊት መሆኑ ነው፡፡ አረንጓዴ ቴክኖሎጂ የአሁኑ ትርጉም ተሰጥቶት ተግባራዊ መሆን በጀመረበት ወቅትም ቢሆን ለአቶ መለስና ኢህአዴግ ሩቅ ነው፡፡ አረንጓዴ ኢኮኖሚ በተደራጀ መልኩ በተለይም በተቋማት አነሳሽነት የጀመረው እ.ኤ.አ በ1980ዎቹ መጀመሪያ ላይ ነው፡፡ ለአብነት ያህል እ.ኤ.አ በ1980 ዓለም አቀፍ የተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ ህብረት አገራት ቀጣይነት ያለው እድገት ማስመዝገብ እንዲችሉ ለማድረግ በሚል ይህን የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ተግባራዊ ማድረግ እንዳለባቸው በጥናቱ ላይ እስቀምጧል፡፡

ከ12 አመት በኋላ እ.ኤ.አ በ1992 (አቶ መለስ ስልጣን በያዙ ከአንድ አመት በኋላ ሲሆን በስብሰባው አልነበሩም) በብራዚሏ ሪዮ ዲጀኔሮ በተካሄደው ስብሰባ ለአረንጓዴ ኢኮኖሚ ትልቅ ትኩረት ተሰጥቶት እንደነበር መረጃዎች ይጠቁማሉ፡፡ በመሆኑም ኢህአዴግ አቶ መለስ አረንጓዴ ኢኮኖሚን ለዓለም በአማራጭነት ያቀረቡ በሚል የሚያቀርበው ሙገሳ ከእውነት የራቀ ነው፡፡ አቶ መለስ በቅርብ አመታት አፍሪካን ወክለው በተለያዩ መድረኮች ስለ አየር ንብረት ድርድር አድርገዋል፡፡ ይህም ቢሆን ኢትዮጵያ በአፍሪካ ህብረት ያላት መቀመጫና ተደማጭነትንም ጭምር ያገናዘበ ነው፡፡
አቶ መለስ በዓለም አቀፍ መድረክ የማሳመን ብቃት ስላላቸው ነው ቢባል እንኳ በድርድሩ ወቅት የሚያቀርቡት ማሳመኛ የአፍሪካ አገራት ባለሙያዎች፣ መሪዎችና ሌሎች አካላት ተወያይተው የተስማሙበትን ሀሳብ ነው፡፡ በአንድ ወቅት አቶ መለስ በዓለም አቀፍ የአካባቢ ጥበቃ መድረክ አፍሪካ ልታገኝ ይገባት የነበረውን 30 ቢሊዮን በላይ ዶላር ጥቅም 10 ቢሊዮን እንዲሆን አድርገዋል በሚል ከሱዳንና ከሌሎች ልዑካን ተቃውሞ እንደደረሰባቸው ስናስታውስ ደግሞ አዲስ ፈጠራ ማበርከት ብቻ ሳይሆን አፍሪካውያን የተስማሙበትንም እንዳላስፈጸሙ እንመለከታለን፡፡ በ2005 ዓ/ም አፍሪካን የወከለችው ኢትዮጵያ ስለአረንጓዴ ኢኮኖሚ ለተባበሩት መንግስታት አቅርባ ተቀባይነት ማግኘቷ ተዘግቧል፡፡ ይህም ቢሆን ጥቃቅን ማሻሻያ ረቂቅ እንጂ የአጠቃላይ አረንጓዴ ኢኮኖሚው ጠንሳሽ ሊያደርጋት አይችልም፡፡ ኢትዮጵያ ብቻ ሳትሆን በርካታ አገራት አጀንዳና ሃሳብ ያቀርባሉ፡፡ ማሻሻያና የመሳሰሉትን በማቅረባቸው ግን ራሳቸውን የዋናው ሀሳብ አመንጭ አድርገው ሲያቀርቡ አይታዩም፡፡

በነገራችን ላይ ህወሓት በርሃ በወጣባቸው በመጀመሪያ አመታት ደርግ ‹‹አረንጓዴ ልማት›› በሚል ሰፋፊ እርሻዎች ልማት ጀምሮ እንደነበር ይነገራል፡፡ በወቅቱ አሁን ለአቶ መለስ መታሰቢያ የየመስሪያ ቤቱ ሰራተኛ አትክልት ከሚተክለውም በላይ ኢትዮጵያውያን በግድ ምግባቸው ብቻ እየተቻላቸው ያለሙ ነበር፡፡ ይህ ኢትዮጵያውያን ተገደው ያሉሙት የነበረው ልማት ለደርግ ‹‹አረንጓዴ ኢኮኖሚ›› መሆኑ ነው፡፡ በእርግጥ ኢህአዴግም ይህን ያህል ተግባር ቢፈጽም ከደርግ ያልተናነሰ ራዕይ ጨምሮበት ለፕሮፖጋንዳ ሊጠቀምበት እንደሚችል የሚያጠራጥር አይደለም፡፡

ኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት ይህን የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ተግባዊ እያደረጉ ከሚገኙ አገራት መካከል በመጨረሻዎቹ ረድፍ የተመደበች አገር ነች፡፡ ኢትዮጵያ ባለፈው 40ና 50 አመት ከ40 በመቶ በላይ የደን ሽፍን እንደነበራት ይነገራል፡፡ በህዝብ ብዛትም ሆነ በሌሎች ምክንያቶች ከ20 አመት በፊት ይህ የደን ሽፋን ከ3-4 በመቶ ይሆን እንደነበር በመስኩ የተደረጉ ጥናቶች ያስረዳሉ፡፡ አሁን ከዚህም በታች ወርዷል፡፡ ለ99 አመት ለአረብ፣ ህንድና ቻይና ባለሀብቶች እየተሰጠ ያለው በደን የተሸፈነ መሬት ሲመነጠር ድግሞ ይህን የደን ሀብታችን በእጅጉ እንደሚያመናምነው አያጠራጥርም፡፡

የኢትዮጵያ መንግስት አረንጓዴ ኢኮኖሚን በመርህ ደረጃ እፈጽማለሁ ቢልም ተግባራዊነቱ ግን ገና በእንጭጭ ላይ ነው፡፡ ከተቋማቱ ጀምሮ ለአረንጓዴ ኢኮኖሚ ዝግጁ አለመሆኑን የሚያሳይ ነው፡፡ አለብነት ያህል፣ አብዛኛዎቹ ክልሎች የደን ልማት በግብርና ሚንስትር ስር የሚገኝ ነው፡፡ በመሆኑም የግብርና ሚንስተር በተቻለ መጠን አገሪቱን መሬት እንዲታረስ ማድረግ ነው፡፡ የደን ጥበቃ ደግሞ ደንን ማሰጠበቅ፡፡ እነዚህ ሁለቱ የሚጋጩ ለጥዕኮዎች አላቻው ናቸው፡፡ በተለይ ኢንቨስትመንትን ለማስፋፋት በሚል ለኢንቨስተሮች ሰፋፊ መሬቶችን የሚሰጡት የክልል ቢሮዎች ለደን ልማትና ለአረንጓዴ ኢኮኖሚ ምንም ዝግጅት የላቸውም፡፡ ለምሳሌ ያህል ጋምቤላ ብንወስድ፤ ለውጭ ባለሀብቶች እየተሰጠ ያለው መሬት ታርሶ የማያውቅና በደን የተሸፈነ እንደሆነ ይነገራል፡፡ እስካሁን በጋምቤላ ብቻ ከሲውዘርላንድ የሚበልጥ የቆዳ ስፋት ያለው መሬት ለውጭ ባለሀብቶች ተሰጥቷል፡፡ እነዚህ የውጭ ባለሀብቶች የሚጠቀሙበት ኬሚካል የአካባቢውንና የአገሪቱን የአየር ንብረት ይበክላል፡፡ ይህ ሰፊ ደንን እያስመነጠሩ መሬትን በሲጋራ ዋጋ መሸጥ፣ በኬሚካል ማስበከል አቶ መለስ ጀምረውት ሌሎቹ በ‹‹ራዕይ›› እያስቀጠሉት ነው፡፡ እንዲህ ደን እየወደመ፣ የአየር ንብረት እየተበከለ፣ አፍሪካውያን ለተበከለው ይከፈለን የሚሉትን ሰያስፈጽሙ አቶ መለስና ኢህአዴግ ከአረንጓዴ ቴክኖሎጂ ጋር ምን እንደሚያገናኛቸው አይገባኝም፡፡

Health: ሸንቃጣማነትን በቀላሉ የሚያጎናጽፍሽ ስልቶች

$
0
0

‹‹ቅጥነት ውበትም ጤንነትም ነው›› የሚለው መርህ በብዙዎች ዘንድ ተቀባይነትን ያገኘ ይመስላል፡፡ አባባሉ ትክክል ስለሆነ ተቀባይነትን ማግኘቱ አይከፋም፡፡ ከመጠን ያለፈ ውፍረትን መቀነስ በልብ ህመም፣ በደም ግፊትና በስኳር በሽታ የመጠቃት እድልን ለመቀነስ ስለሚያስችለን ማንኛውም ሰው ውፍረቱን እንዲቀንስ ይበረታታል፡፡ ውፍረትን መቀነስ የሚመከር ቢሆንም ግን ክብደታቸውን እንዴት መቀነስ እንዳለባቸውም ሊያውቁ ይገባል፡፡ ውፍረታቸውን ለመቀነስ ከሚያግዙ ስልቶች ውስጥ ክብደትን የሚጨምሩ መመገብ የሌለባቸውን እና መመገብ ያለባቸውን የምግብ አይነቶች መለየት፣ የመመገቢያ ሰዓት መለየትና የአካል ብቃት እንቅስቃሴ ማድረግ ይጠቀሳሉ፡፡ አንድ ሰው ክብደቱን ለመቀነስ ከመወሰኑ በፊት ግን መጠነኛ የሆነ ክብደት ለመያዝ የክብደቱን መጠን ሳይንሳዊ በሆነ ሂደት መለየት አለበት፡፡

ክብደትን ለመለየት የሚረዱ ሁለት ሳይንሳዊ መንገዶች አሉ፡፡ እነኚህም አንደኛው በወገብ መጠን ዙሪያ በመለካት ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ የሰውነት ክብደት መጠንና በሽታን የማስከተል አቅም ማሳያ (Body mass index) ነው፡፡

bodyየወገብ መጠን ዙሪያ፡- የወገብ መጠነ ዙሪያ የአንድ ሰው ስብ የበዛበትን የሰውነት ክፍሉን ለመለየት ይረዳል፡፡ በወገባቸው አካባቢና ከወገባቸው በላይ ወፍራም የሆኑ ሰዎች ‹‹አፕል›› ቅርፅ ያላቸው ሲባሉ ከወገባቸው በታች ወፍራም የሆኑ ሰዎች ደግሞ ‹‹ፒየር›› ቅርፅ ያላቸው ይባላሉ፡፡ ከወገብ በላይ ወፍራም የሆኑ ሰዎች ከወገባቸው በታች ወፍራም ከሆኑ ሰዎች ይበልጥ ውፍረታቸውን ለመቀነስ ጥረት ማድረግ አለባቸው፡፡ ምክንያቱም ከወገብ በላይ መወፈር በቀላሉ ለደም ግፊት፣ ለስኳር፣ ለካንሰር እና ለልብ ህመም ያጋልጣል፡፡ ይህ ሊሆን የቻለው ወገብ አካባቢ የተከማቸ ስብ በቀላሉ ስለሚፈረካከስና በደም ቧንቧ ውስጥ የመከማቸት ባህሪ ስላለው ነው፡፡

የሰውነት ክብደት መጠንና በሽታን የማስከተል አቅም ማሳያ (Body maxindex)

ክብደትዎ በጥሩ ሁኔታ ላይ እንደሚገኝ ወይም ምን ያህል ክብደትዎን መቀነስ እንዳለቦት ለማወቅ የሰውነት ክብደት መጠንና በሽታን የማስከተል አቅም ማሳያ ቀመርን መጠቀም አለቦት፡፡ ቀመሩ በሚከተለው መንገድ ይቀመጣል፡፡ የሰውነት ክብደት በሽታን የማስከተል አቅም ማሳያ = ክብደት
ቁመት X ቁመት
የዚህ ድምር ውጤት በ19 እና በ24 መሀል ከሆነ ሰውየው ለጤናው ጥሩ የሆነ ክብደት እንዳለው ያሳያል፡፡ የድምሩ ውጤት ከ25 እስከ 29 ከሆነ ሰውየው ውፍረቱን መቀነስ አለበት፡፡ የድምሩ ውጤት በ30 እና በ40 መሀል ከሆነ ሰውየው ውፍረቱ ለጤናው አስጊ መሆኑን ተረድቶ በፍጥነት ክብደቱን ለመቀነስ ጥረት ማድረግ አለበት፡፡

ክብደትን ለመቀነስ የሚረዳ ምርጥ ስልት

አንድ ክብደቱን ለመቀነስ የሚፈልግ ሰው የአኗኗር ዘይቤውን መቀየር አለበት፡፡ ይኸውም የሰውነቱን ስብ ለማቃጠል የአመጋገብ ሁኔታውንና የሚመገበውን የምግብ አይነት መቀየርና አካላዊ እንቅስቃሴ ማድረግ አለበት፡፡
የሚከተሉት መርህዎች ክብደቱን ለመቀነስ የሚፈልግ ማንኛውም ሰው ራሱን ሳይጎዳ የሚፈልገውን ያህል ክብደት ለመቀነስ ያግዙታል፡፡
አንድ ክብደቱን ለመቀነስ የሚፈልግ ሰው ሴትም ሆነች ወንድ የሚከተሉትን መርህዎች በመከተል ራሳቸውን ሳይጎዱ የሚፈልጉትን ያህል ክብደት ለመቀነስ ይችላሉ፡፡
– በመጀመሪያ ክብደቶን ለመቀነስ እቅድ ያውጡ፡፡ እቅዶን ጥሩ ስሜት በተፈጠረብዎ ቀን ይጀምሩ፡፡

– የሚመገቡትን የምግብ አይነት ይምረጡ፡፡ ክብደታቸውን ለመቀነስ የሚያስቡ ብዙዎቹ ወፋፍራም ሰዎች የሚመገቡት የምግብ አይነት ለውፍረታቸው መንስኤ መሆኑን አይረዱም፡፡ አንድ ወፍራም የሆነ ሰው በሳምንት ከ0.5 እስከ 1 ኪሎ ግራም ለመቀነስ በፊት ይመገብ ከነበረው በቀን ከ500 እስከ 100 ካሎሪ መቀነስ አለበት፡፡ ረሀብዎን ለማስታገስ ከመመገቢያ ሰዓት ውጭ በሚቀማምሱበት ወቅትም ሆነ በተገቢው መንገድ ቁርስ፣ ምሳና ራትዎን ሲመገቡ አትክልት፣ ፍራፍሬ፣ ጥራጥሬና ሌሎች ካሎሪ ያልበዛባቸውን ለጤና ተስማሚ የሆኑ ምግቦችን ይመገቡ፡፡ ይህ ማለት ግን ወፍራም ሰዎች ሙሉ ለሙሉ ካሎሪ የያዙ ምግቦችን መመገብ የለባቸውም ማለት አይደለም፡፡ ማንኛውም ሰው አካሉ ተመጣጣኝ የሆነ ንጥረ ነገር እንዲያገኝ በቀን ቢያንስ 1200 ካሎሪ ማግኘት አለበት፡፡
– በምግብ ሰንጠረዥዎ ውስጥ ስብ የሆኑ ምግቦችን ዝርዝር ከ30 በመቶ ወይም ከ20 በመቶ በታች ያድርጉ፡፡

– ወፍራም ከሆኑ ጥብሳ ጥብሶችን፣ ከምግብ በፊት የምግብ ፍላጎትን ለመጨመር የሚወሰዱ ቅባትነት የበዘባቸውን መቆያዎችን እንዲሁም ማርጋሪንና ማዮኒዝን የመሰሉ ከፍተኛ ስብ የያዙ ምግቦችን መመገብ በመተው ወይም የሚመገቡትን መጠን ለመቀነስ ይችላሉ፡፡
– በተለመደው የመመገቢያ ሰዓትዎ ሳይመገቡ አያሳልፉ፡- ክብደታቸውን ለመቀነስ በማሰብ አንዳንድ ሰዎች ቁርሳቸውን፣ ምሳቸውን ወይም ራታቸውን ሳይበሉ የሚመገቡትን የምግብ መጠን ለመቀነስ ይሞክራሉ፡፡ በእንዲህ አይነት መንገድ ክብደትን ለመቀነስ መሞከር አይመከርም፡፡ በየሰዓቱ መመገብ የተስተካከለ የምግብ ፍላጎት እንዲኖረን ከማድረጉ በተጨማሪ ቁርስ መብላት የሰውነታችን ምግብን የማቃጠል ብቃት እንዲጨምር ስለሚያደርግ በርካታ ካሎሪዎችን ለማቃጠል ያግዛል፡፡
– በየዕለቱ የተመገቡት የምግብ መጠን በወረቀት ላይ ይፃፉ፡- የተመገቡትን የምግብ ዝርዝር በወረቀት ላይ የሚፅፉ ሰዎች የበሉትን የምግብ ብዛት ለመመጠን ስለሚያስችላቸው በአጭር ጊዜ ክብደታቸውን ለመቀነስ ይችላሉ፡፡
– ከመጠን በላይ እንዲበሉ የሚያደርጉትን ነገር ይለዩ፡- ብዙ እንዲበሉ የሚያደርጉት ምንድነው? ከስሜትዎ ጋር የተያያዘ ነው? ከምግቦቹ አይነት ጋር የተያያዘ ነው? ወይስ ከስራዎ ጋር የተያያዘ ነው? ዝም ብለው ሳያስቡት ከመጠን በላይ እንዲበሉ የሚያደርጉት ሁኔታዎች አሉ? ለምሳሌ ቴሌቪዥን ሲያዩ ወይም ጋዜጣ ሲያነቡ ብዙ ይበላሉ?

– የሚመገቡትን ብቻ ሳይሆን የሚጠጡትን ፈሳሽ ይቆጣጠሩ፡- በተቻሎ አቅም የአልኮል መጠጦችን አይጠጡ፡፡ ምክንያቱም ብዙዎቹ የአልኮል መጠጦች በውስጣቸው ከፍተኛ ካሎሪ ከመያዛቸው በተጨማሪ የምግብ ፍላጎትን ከመጠን በላይ ስለሚጨምሩ የሚመገቡትን የምግብ መጠን መቆጣጠር እንዲያቅትዎ ያደርጎታል፡፡ ወተት እና የፍራፍሬ ጭማቂዎችም የስብ ክምችታቸው ዝቅተኛ ቢሆንም በውስጣቸው ከፍተኛ ካሎሪ በመያዛቸው አብዝቶ መጠጣት አይገባም፡፡
– አብዛኞቹ ጣፋጭ ምግቦች ከፍተኛ ካሎሪና ስብ የያዙ ስለሆኑ ጣፋጭ የሆኑና ስኳርነት የበዛባቸውን ምግቦች ከመመገብ ይቆጠቡ፡፡
– ቀስ እያሉ ይመገቡ፡- ቀስ እያሉ መመገብ ሆድዎ ሲሞላ እንዲታወቅዎና ከመጠን በላይ እንዳይመገቡ ይረዳል፡፡
– እየተመገቡ ሌላ ስራ አይስሩ፡- ለምሳሌ ቴሌቪዥን እያዩ ወይም እያነበቡ የሚመገቡ ከሆነ ሳይታወቅዎ ብዙ ይባላሉ፡፡
– የረሃብ ስሜት ሳይፈጠርብዎ ዝም ብለው አይብሉ፡- አንዳንዴ ዝም ብለው መብላት ሊያምሮት ይችላል፡፡ እንዲህ አይነቱ አምሮት ከጥቂት ደቂቃ በኋላ ስለሚጠፋ በትዕግስት ያሳልፉት፡፡
– በየቀኑ ክብደትዎን አይለኩ፣ ለመቀነስ የሚፈልጉትን የክብደት መጠን ይወስኑ፣ ውሳኔዎትንም በጊዜ ገደብ በአጭር እና በረጅም ጊዜ ይከፋፍሉት፣ ለምሳሌ 18 ኪሎ ግራም ለመቀነስ ከፈለጉ በወር 3 ኪሎ ግራም ለመቀነስ ይጀምሩ፣ ቀስ በቀስ ከተወሰነ ወር በኋላ 18 ኪሎ ግራም ለመቀነስ ይችላሉ፡፡ በአንድ ጊዜ 18 ኪሎ ለመቀነስ አስበው በየቀኑ ክብደቶን የሚመዝኑ ከሆነ ተስፋ ቆርጠው ክብደትዎን ለመቀነስ የዘረጉትን እቅድ ተግባራዊ የማድረግ ሞራልዎ ይጠፋል፡፡ ክብደትዎን ለማወቅ በሳምንት ወይም በሁለት ሳምንት አንድ ጊዜ ከተመዘኑ ይበቃዎታል፡፡

እነ አባዱላ ፓስፖርታቸውን ተቀምተዋል- ኦህዴድና ብአዴን ይጠይቃሉ፤ ህወሓት ይመልሳል

$
0
0

ነገረ ኢትዮጵያ

ከአመታት በፊት የገዥው ፓርቲ አባል ሳይሆን በመንግስት ስራ ላይ ተሰማርቶ ይሰራ ነበር፡፡ 1997 ዓ.ም በኋላ ግን በዚህ አቋሙ አልቀጠለም፡፡ ‹‹አንዴ ቅንጅት ሌላ ጊዜ ደግሞ ኦነግ እያሉ ስም ሲለጥፉብኝ ‹ከዚህ ሁሉ!› ብየ ኦህዴድን ተቀላቀልኩ›› ይላል ካድሬው ለነገረ ኢትዮጵያ፡፡ ከዚህ በኋላ ባሉት ጊዜያት ደመወዝና እድገት በእጥፍ ተጨምሮለታል፡፡ የትምህርት እድል ተሰጥቶታል፡፡ በተቃራኒው ደግሞ ኦህዴድም ሆነ ኢህአዴግ ህዝብ ላይ የሚፈጽሙትን በደል በቅርብ ርቀት ተገኝቶ ተከታትሏል፡፡

ካድሬው እንደሚለው ከእነ አባዱላና መሰል ፖለቲከኞች ውጭ የኦህዴድ ካድሬዎች በፓርቲያቸው እምነት የላቸውም፣ በህወሓት በደል በእጅጉ ተማርረዋል፡፡ የ‹‹ብአዴኖችም ከእኛ የሚለይ ነገር የለውም፡፡ ተመሳሳይ ነው፡፡›› ይላል ካድሬው፡፡

በበርካታ ጉዳዮች ‹‹ፓርቲዬ›› ከሚለው ኢህአዴግ እንደሚለይ ቢገልጽም በአንድ ጉዳይ ግን ይስማማማል፡፡ ‹‹ጥያቄ የሚያቀርብ ካድሬ አንድም ኦነግ አሊያም የድሮው ቅንጅት አካል የነበረ ፓርቲ ወይንም ትምክተኛ ተብሎ ስም ይሰጠዋል፡፡ ኦነግ ወይንም ‹‹ቅንጅትነት/ትምክተኝነት›› ጥያቄ ማንሳት ከሆነ የኦህዴድ ካድሬዎች ሲገለጡ ኦነጎች ናቸው፡፡ ብአዴኖቹ ደግሞ እንደዛው ቅንጅት/ትምክተኛ ናቸው ማለት ነው››፡፡ በዚህ ጉዳይ ካድሬው የድሮው ጠቅላይ ሚኒስትር ‹‹ኦህዴድ ሲገለጥ ኦነግ ነው!›› በሚለው ይስማማል፡፡

ካድሬው ለነገረ ኢትዮጵያ እንደገለጸው በተለይ የብአዴንና የኦህዴድ ካድሬዎች በህወሓት ጫና ከመቼውም በላይ ተማርረዋል፡፡ ‹‹አዛዡም ናዛዡም ህወሓት ነው፡፡ ትጠይቃለህ፡፡ ስም ይሰጥሃል፡፡›› የሚለው የኦህዴድ ካድሬ፤ የኦህዴድና የብአዴን ካድሬዎችም ሆነ ባለስልጣናት ይህ ነው የሚባል ተጽዕኖ እንደሌላቸው ከተሞክሮው ይመሰክራል፡፡ ‹‹ብአዴንና ኦህዴድ ይጠይቃሉ፡፡ ህወሓት ይመልሳል፡፡ የብአዴንና የኦህዴድ ባለስልጣናት ካድሬዎቹ የሚጠይቋቸውን ጥያቄዎች እንኳን በራሳቸው መመለስ አልቻሉም፡፡ ህወሓት ብአዴንም፣ ኦህዴድም፣ ኢህአዴግም ሆኖ ሁሉም የሚጠይቀውን ጥያቄ ይመልሳል፡፡ እንዲያው እድል ተሰጥቷቸው የሁለቱ ፓርቲዎች ፖለቲከኞች ቢመልሱ እንኳ የህወሓት ተራ ካድሬም ቢሆን የሆነ ነገር ያስተካክላል፡፡ ኦህዴድና ብአዴን ብቁ አለመሆናቸውን ለማሳየት የሚያደርገው ነው፡፡››

ካድሬውን ‹‹ኢህአዴግን ምን የሚያሰጋው ይመስልሃል?›› በሚል ከነገረ ኢትዮጵያ ለቀረበለት ጥያቄም የመጀመሪያው ያደረገው ፓርቲው ውስጥ ያለውን ክፍፍል ነው፡፡ ‹‹አብዛኛው የኢህአዴግ ካድሬ እንደ እኔ ፓርቲው ያደርስብኛል ካለው አደጋ ለመዳን አሊያም ለገንዘብ የተቀላቀለ ነው፡፡ አያምንበትም፡፡ ሁሉም ቀን ነው የሚጠብቀው፡፡ ወደ ህዝብ ሲቀርቡ በመካከላቸው ችግር እንደሌለ ያስመስላሉ እንጅ የኢህአዴግ አባል ፓርቲዎች በመካከላቸው ከፍተኛ ቅራኔ አለ፡፡ ለምሳሌ ያህል በዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ላይ የተወሰደው እርምጃ የኦህዴድ ካድሬዎችን አስቆጥቷል፡፡ እስካሁን ይመለስላቸው አይመለስላቸው ባላውቅም በወቅቱ እነ አባዱላ ፓስፖርታቸውን እንደተቀሙ ሰምቻለሁ፡፡ ይህ አንድ ቀን የሚፈነዳ ይመስለኛል፡፡››

ሌላው ይላል ካድሬው ‹‹ህዝብ በፓርቲው እምነት እንደሌለው ሁላችንም እናውቃለን፡፡ ህዝብ ገንፍሎ የሚወጣ ይመስለኛል፡፡ በእርግጥ አሁን ህዝቡ ዝምታን መርጧል፡፡ በተለያዩ ጊዜያት ህዝብን ለማሳመን ወይንም ለማስተማር በሄድኩበት አጋጣሚ ከዝምታው በስተጀርባ ህዝብ ለፓርቲው ጥላቻ እንዳለው ለማየት ችያለሁ፡፡ በቅርቡ በተለያዩ የኦሮሚያ ዩኒቨርሲቲዎች ስልጠና የተሰጣቸው ተማሪዎች ሰነዱን አቃጥለው ስለ ነጻነት ዘምረዋል፣ ፓርቲው አብጠልጥለዋል፡፡ ይህ ሁሉ ሲደማመር አንድ ቀን ህዝብ ገንፍሎ የሚወጣ ይመስለኛል››

 

negere

የቦሌ ክፍለ ከተማ መምህራን በትግላቹህ ኮርተናል (የኢትዮጵያ መምህራን ድምፅ ይሰማ ጊዜያዊ ኮሚቴ)

$
0
0

የኢትዮጵያ መምህራን ድምፅ ይሰማ ጊዜያዊ ኮሚቴ
አዲስ አበባ ኢትዮጵያ

በመጀመሪያው ተቃውሞ ካድሬዎች እርስ በእርስ ተጣሉ

ዛሬ በተጀመረው የመምህራን ስልጠና አዲሱ የትግል ስልታችን ተግባራዊ ሆኖ ውጤቱን ከመጀመሪያው መታዘብ ችለናል
ትላንት ከየኢትዮጵያ መምህራን ድምፅ ይሰማ በተላለፈው የትግል ስልት አንድ መሰረት በቦሌ ክፍለ ከተማ ቦሌ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የተሰበሰቡ መምህራን ምንም አይነት አስተያየት ከመስጠት በመቆጠባቸው ምክንያት ስብሰባው ሲጠናቀቅ በመምህራኑ ድርጊት የተበሳጩት ሰብሳቢዎች እርስ በእርስ ተጣልተው በፖሊስ ሊገላገሉ ችለዋል
በሌሎችም ክፍለ ከተሞች ተቃውሞው ይቀጥል ዘንድ ኮሚቴው ጥሪውን ያቀርባል

ድል ለሰፊው ህዝብ

ክቡራት እና ክቡራን የሙያ ባልደረቦቻችን መምህራን ሰላሙ ይብዛላችሁ:: የእናንተው የኢትዮጵያ መምህራን ድምፅ ይሰማ ጊዜያዊ ኮሚቴ የእኛን የመምህራንን ድምጽ ለማሰማት የተለያዩ ስራዎችን እየሰራ መሆኑ ይታወቃል:: እስካሁን ባደረገው ትግል በርካታ ማስፈራሪያ እና ዛቻ በሰልጣን ላይ ካለው መንግስት ቢደርስብንም ትግሉን ስንጀምር ጉዟችን ረጅም እንደሆነ በማወቃችን በየጊዜው የሚደርሱብንን በድሎች ተሸክመን እዚህ ደርሰናል ሆኖም የህወሀት የደህንነት ሀይሎች በኮሚቴው ላይ እያደረሱት ያለው ኢሰብአዊ ድርጊት አካሄዳችንን እንድንቃኝ አስገድዶናል::
ከአሁን በኋላ ትግላችን ወደ ኋላ ሊመለስ አይገባም ትግላችን ከመከላከል ወደ ማጥቃት ሊሻገር ይገባዋል::

በዚህም መሰረት ከነገ ማለትም ከመስከረም 5,2007 አ.ም ጀምሮ በአዲስ መንገድ ለመንቀሳቀስ ጊዜያዊው ኮሚቴ የተለያዩ የትግል ስልቶችን ቀይሶ የሙያ ባልደረቦቻችንን ለማንቀሳቀስ እቅድ ነድፎ ወደ ስራ መግባቱን ይገልጻል::
በዚህም መሰረት ከነገው ከመስከረም 5 ጀምሮ የሚካሄዱ የተቃውሞ አካሄዶች:-
1. ከማንኛውም የኢህአዴግ አባል መምህር ጋር ያለንን ግኑኝነት ማቋረጥ::
የኢህአዴግ አባላት እንደሆኑ የምናውቃቸውን ግለሰቦች እየመረጥን ከማንኛውም ማህበራዊ ግኑኝነቶች ማግለል ማለትም ሰላምታ አለመለዋወጥ: በተሰበሰብንበት አካባቢ አባላቶቹ መጥተው ሲቀላቀሉ መበተን ወ.ዘ.ተ የመሳሰሉትን የማግለያ መነገዶች በመጠቀም ከህዝቡ እንዲገለሉ እና ብቻቸውን እንዲቀሩ ማስቻል::
2. ነገ በሚጀመረው የመምህራን ስልጠና ላይ ተቃውሟችንን ለማሰማት ስበሰባው ላይ በተደጋጋሚ ሰበብ እየፈጠሩ መውጣት: ስብሰባውን መከታተል አቁመን መጽሀፍት እና ጋዜጣ ማንበብ እንዲሁም በስብሰባው ላይ ምንም አስተያየትም ሆነ ድጋፍ ከመስጠት መቆጥብ ይኖርብናል::
ማሳሳቢያ ይህንን ስናደርግ የኢህአዴግ ቅጥረኞች እየነጠሉ እንዳያጠቁን ጥንቃቄ ማድረግ የሚጠበቅብን ሲሆን ይህንን መረጃ ለቀሪው ባልደረቦቻችን ሼር በማድረግ ሁሉም የትግሉ አካል እንዲሆን የበኩላችንን አስተዋጽኦ እናድርግ ::

 

18


በ 2007 ዓ.ም ለሚደረገው ሃገራዊና ክልላዊ ምርጫ ሚሊሻዎች ልዩ ተልዕኮ እንደተሰጣቸው ተገለጸ

$
0
0

2007 electionኢሳት ዜና ፦ በ2007ዓ.ም ለሚደረገው ሃገራዊና ክልላዊ ምርጫ ህብረተሰቡ ለተለያዩ ተቀናቃኝ ፓርቲዎች ድምፁን እንዳይሰጥ ለማፈን በሚያስችል ሁኔታ በክልሉ የሚገኙ ሚሊሻዎች ልዩ ተልዕኮ እንደተሰጣቸው ተገለጸ የአማራ ብሄራዊ ክልል መንግስት ሚሊሽያ ጽህፈት ቤት ምክትል ኃላፊ አቶ መኳንንት መልካሙ ሰሞኑን ለታማኝ አመራሮች በሰጡት ድርጅታዊ መግለጫ ላይ በያዝነው ዓመት በሚካሄደው ምርጫ ህዝቡ የተለያየ ፅንፍ በመያዝ ገዢው ፓርቲ ላይ ስጋት የሚፈጥሩ ችግሮችን በማስወገድ ሙሉ በሙሉ አሸናፊ ለማድረግ የሚያስችለውን ቅድመ ዝግጅት ማጠናቀቁን ሲናገሩ ተደምጠዋል። አቶ መኳንንት ባለፈው ዓመት ለዚሁ ልዩ ተልዕኮ ከ360 በላይ ለሆኑ የሚሊሽያ አመራሮችና ባለሙያዎች በሁለት ዙር ፤ በወረዳ ደረጃ ላሉ የሚሊሺያ አባላትም ለአምስት ተከታታይ ቀናት በሁለት ዙር ስልጠና መሰጠቱን ተናግረዋል። በክልሉ ውስጥ በሚገኙ ከ3 ሺህ 600 በላይ በሆኑ ቀበሌዎች ላሉ የሚሊሽያ አባላትም ልዩ ተልዕኮውን እንዴት ማሳካት እንደሚችሉ የሚያግዝ ስልጠናዎች መሰጠታቸውን ምክትል ሃላፊው ለታማኝ የስርአቱ ደጋፊዎች ገልጸዋል።

በክልሉ ያሉ የሚሊሽያ አባላት ከህዝቡ የተወጣጡ እና የገዢው መንግስት ደጋፊዎች መሆናቸው ስለሚታመን ጠዋትና ማታ ከህብረተሰቡ ጋር በመገናኘት በየቀበሌው ካሉ ልዩ ልዩ የወጣት፣ የሴቶች እና የአርሶ አደሩ አደረጃጀቶችን በመጠቀም የመራጩን ህዝብ አመለካከት የመቀየር ስራ እንዲሰራ መታዘዙን፣ ይህ አሰራር ህዝቡ ታማኝነቱንና ድምጹን ለገዢው ፓርቲ የሚሰጥ መሆኑን የማረጋገጥ ሂደቱን ሊያሳካ ይችላል ተብሎ እንደታመነበት ለታማኞች ተናግረዋል። በተለያዩ ጊዜያት የተሰጡትን ስልጠናዎች ለማካሄድ ከ22 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የጠየቀ ቢሆንም፣ ከዚህ ወጪ ውስጥ ከ15 ሚሊዮን ብር በላይ ህብረተሰቡ እንዲሸፍን መደረጉን፣ ገንዘብ በእጁ የሌለው ድሃው ህብረተሰብ ሳይቀር በግ ፣ ፍየል ፣ ዶሮና እህል እንዲያዋጣ በማድረግ ለሚሊሺያው ስልጠና መሰጠቱን ባለስልጣኑ ገልጸዋል።

በቀጣይም ተመላሽ ከሆኑ ወታደሮች ውስጥ የተሻለ የድርጅት ፍቅር ያላቸውን በመለየት ወደ ሚሊሽያው የመቀላቀል ስራ እየተሰራ እንደሆነ በዚሁ ዝግ ውይይት ተናግረው ፣ ወታደሮቹ በየገጠር ቀበሌው ሲሰማሩ ልዩ ልዩ ጥቅሞችን ከአርሶአደሩ ሊያገኙ የሚችሉበትን አሰራር ለመዘርጋት ግፊት የማድረግ ሃሳብ ወደ አመራሩ ዘንድ እንደወረደም አስረድተዋል። አቶ መኳንንት የግልና የመንግስት ተቋማት ጥበቃዎችና ሚሊሺያው ከላይ እስከታች የአመለካከት ችግር ያለባቸው በመሆኑ እና ተልዕኮ የሚሰጣቸው ከጸረ ሰላም ሃይሎች በመሆኑ ለአካባቢው ልማት ጠንቅ መሆናቸውን ገልጸዋል። ተከታትለው አንዳንድ ርምጃዎችን ለመውሰድ በአመራሩ መካከል መግባባት ላይ መደረሱንም ተናግረዋል። ስማቸውን መግለጽ ያልፈለጉ በዳንግላ ዙሪያ ወረዳ የሚገኙ አንዳንድ አመራሮችና የሚሊሺያ አባላት ሚሊሺያው ከገዢው መንግስት ጥቅም ይልቅ የህብረተሰቡን ጥቅም በማስቀደም ከታሪክ ተወቃሽነት ነጻ እንሆናለን ብለዋል። የድምጽ መረጃውን ለላኩልን የሚሊሺያ አባላት ምስጋናችንን እንገልጻለን።

ከአቶ ገብሩ አስራት አዲስ መጽሐፍ የተገኙ 9 ነጥቦች

$
0
0

የቀድሞው የትግራይ ክልል ፕ/ት አይተ ገብሩ አስራት “ሉዓላዊነትና ዴሞክራሲ በኢትዮጵያ” የሚል አዲስ መጽሐፍ ማሳተማቸውና በዋሽንግተን ዲሲ ሴፕቴምበር 1 ቀን 2014 እንዳስመረቁ ዘ-ሐበሻ መዘገቧ ይታወሳል። በዚህም መሥረት ከመጽሐፉ ውስጥ የተገኙ 9 ነጥቦችን ዘኢትዮጵያ ጋዜጣ አስነብቦናል፤ ሙሉ መጽሐፉን እስክታነቡት ድረስ ነጥቦቹን እነሆ፦
ከመጽሐፉ የተወሰዱ
gebru asrat
1ኛ. ህወሃት በ17ቱ የትግል ዓመታቱ 54ሺ ሰዎች መሞታቸውንና ከነዚህ 90 ከመቶ የሚሆኑት የገጠር ወጣቶች ናቸው። በገጽ 165 ።
2ኛ. “የህወሓት/ኢህአዴግ መሪዎች በሚሊዮኖች የሚገመት ገንዘብ እያፈሰሱ ህዝቡ ትግላቸውን እንደገድለ ሰማዕታት እንዲቀበለው አድርገው በሥልጣን ለመቆየትና ከሞቱም በኋላ ዘለዓላማዊ ክብርና ዝና ለማግኘት መሞክሩን ተያዘውታል። ይህን የህዝብና የሰማዕታት የተጋድሎ ታሪክ ጠቅልለው ለአንድ ሰው ለማሸከም ይሞክራሉ። ሰውየው ከሰውነት አልፎ እንዲመለክ ለማድረግ ይሞክራሉ። ይህን ሁሉ የሚያደርጉትም በአሁኑና በወደፊቱ ተግባሮቻቸው ከመኖር ይልቅ ባለፈው ታሪክ መኖሩ ለሥልጣናቸው ህልውና ጠቃሚ ሆኖ ስላገኙት ነው።(ገጽ 4)
3ኛ. እጅግ የሚያናድደኝ ይህ በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን የሚተላለፈው የዘመነ ምኒልክ የጎፌሬዎች ቀረቶና ሸለላ ነው።- ስብሀት ነጋ ገጽ 303
4ኛ. የደርግ ሠራዊት አባላት በግለሰብ ደረጃ እውቀታቸውንና ክህሎታቸውን በጥቅም ላይ የሚያውሉበትና አዲስ በተደራጀው ሠራዊት ውስጥ በአባልነት የሚቀጥሉበት ሁኔታ ቢመቻች ኖሮ ከፖለቲካው አንጻር ይፈለግ የነበረውን የብሔር ብሄረሰብ ስብጥር ከማሟላትም ሌላ የረጅም ጊዜ ልምዳቸውንና እውቀታቸውን አገራዊ ሠራዊት ለመገንባት ባዋሉት ነበር።222
5ኛ. አሁን ሳጤነው በአብዮታዊ ዴሞክራሲ እምነታችን ምክንያት የመረጃ ፍሰትን ገድበን የአገራችንን የአስተሳሰብ እድገት በመጎተታችንና በማጫጨታችን እጸጸታለሁ። ገጽ 249
6ኛ .. ኢህ አዴግ ተቃዋሚዎችን ለመድፈቅና ለማጥፋት ከሚጠቀምባቸው ስልቶች የአመራር አባላቱንና ከፍተኛ ኃላፊዎችን መቆጣጠር። በጥቅም መግዛትና መደለለል ነው። በክፍያ መዝገብ ስማቸው የሠፈረ አሁን ድረስ ተቃዋሚዎች ነን እያሉ የሚንቀሳቀሱ የማውቃቸው አሉ። የነዚህ ሰዎች ተቀጣሪነት ያወቅኹት በኢሕአዴግ አመራር አባልነቴ ሳይሆን ቅርበት ከነበረኝ የደሐኀንነት አባላት ነውና አሁንም የነዚህን የማውቃቸውን ሰዎች ስም ላለመጥቀስ መርጫለሁ። 251
7ኛ. ኢሕአዴግ አማራው ክልል ውስጥ ሲንቀሳቀስ ጠባቦች መጥተው ሊውጡህ ስለሆነ ከ እነርሱ የሚያድንህ ከኢህ አዴግ ጎን ተሰለፍ ብሎ ይቀሰቅሳል። በኦሮሚያ በትግራይና በሌሎች ክልሎች ደግሞ ትምክህተኞች ዳግም አንሰራርተው ሊውጡህ ነው ኢሕ አዴግን ካልተቀበልክና ካልደገፍክ መቀመቅ ትገባለህ እያለ በማስፈራራት ይቀሰቅሳል። ገጽ 199
8ኛ. የሓየሎም ሞት ገዳዩ ኤርትራዊ መሆኑን እያወሱ ከኤርትራ ከነበረው አለመግባባት ጋር ያያዙታል። ይህ ፍጹም ሊሆን አይችልም ብሎ ለማለትም ያዳግታል። 265
9ኛ. (ስለተባረሩ ኤርትራውያን) ጉቦ እየተሰጣቸው መባረር ያለባቸውን እያስቀሩና መባረር የሌለባቸውን ያባርሩ እንደነበር የሚባረሩት ንብረታቸውን ሲሸጡ ተደራጅተው ንብረቱን በርካሽ ይገዙ እንደነበር ኋላ ላይ ተጋልጧል።…እኛን ፀረ- ኤርትራውያንና ፀረ- ዴሞክራሲያዊ ናቸው እያሉ ሲከሱን የነበሩ ቱባ ባለሥልጣኖች ሳይቀሩ ኤርትራውያን ሲባረሩ ቪላዎቻቸውንና የንግድ ድርጅቶቻቸውን ገዝተው እንደነበር ተራው ዜጋ ሳይቀር ያውቀዋል። ሆኖም የህወሃት/ኢህአዴግ አመራር በአንዱ ወይም በሌላው ከኤርትራውያን ጋር በተያያዘ ወንጀል ተዘፍቀው ስለነበር “በመስተዋት በተሠራ ቤት የሚኖር ሰው በድንጋይ አይጫወትም” እንዲሉ ምንም ማድረግ አልቻሉም። 281

ምንጭ፡ ዘኢትዮጵያ ጋዜጣ

የአቶ ገብሩ አስራት መጽሐፍ ቅኝት –ሉዓላዊነትና ዴሞክራሲ በኢትዮጵያ (ሊያነቡት የሚገባ ትንታኔ)

$
0
0

በዋሽንግተን ዲስና አካባቢዋ ከሚታተመው ከዘኢትዮጵያ ጋዜጣ የተገኘ

Gebru Asrat

አቶ ገብሩ አስራት

ታሪክ የሚታወቀው ሲጻፍ ወይ ሲነገር ነው። መታመን አለመታመኑም የሚያከራክረው ተጽፎ ወይም በሌላ ቅርጹ ተመዝግቦ ሲገኝ ብቻ ነው። የታሪክ ታሪክነቱ ስነ ጽሑፉነቱ ሳይሆን ሁነቱ ክስተቱ በሆነ የጊዜ ገደብ ውስጥ መደረግ መፈጸሙ ነው። ካልሆነ ግን ልብወለድ ድርሰት መሆኑ አይቀርም። ሆነም ቀረ ግን ተፈጽሟል እንዲህ ሆኗል እንዲያ ነበር እያሉ ከነማረጋገጫው የሚነግሩን ታሪክ ዘጋቢዎች አሉ። ለተአማኒነቱ ሲባል ከስሜታዊ ወገንተኝነቱ እንዲጸዳ ታሪክ በታሪክ ሠሪዎች ባይጻፍም፣ እነሱ የሚተዉት ማስታወሻ ግን ለታሪክ ፀሐፊዎች ግሩም ስጦታ መሆኑ የታመነ ነው። አቶ ገብሩ አስራት በዚህ ረገድ ለታሪክ ፀሐፊዎች አንድ ማስታወሻ ትተዋል። መጽሐፉ ሰፕቴምበር 1/2014 በዋሽግንተን ዲሲ በተደረገ አንድ ሥነ ሥርዓት ተመርቋል። ዶ/ር ካሳ አያሌው በመሩት በዚህ የመጽሀፍ ምርቃት ፕሮግራም ላይ ተገኝተው መጽሐፉን የቃኙት አቶ ፈቃደ ሸዋቀናም መጽሐፉ ለሌሎች ፀሐፊዎች፣ ተመራማሪዎች፣ ፓለቲከኞችና አንባቢዎች እርሾ ሊሆን የሚችል ፈር ቀዳጅና አከራካሪ መጽሐፍ ሆኖ አግኝቸዋለሁ” ብለዋል።

እንደተባለውም ማከራከሩ አይቀርምና ታሪክ ፀሐፊዎች ወደፊት ፍሬውን ከገለባ ለይተው እውነቱን ከሐሰት አበራይተው ይህን ያለንበትን ዘመን ይገልጹታል። የታሪክ ማስታወሻ መተው እየተበራከተ ባለበት በዚህ ዘመን ዘመኑን አሳምሮና ወክሎ የሚገልጸው ታሪክ የትኛው እንደሆነ ማወቁ ይቸግረን ይሆናል።
ቢሆንም ነገሮች በፍጥነት መደበላለቅ በያዙበት በዚህ ዘመን የተደበላለቀ ስሜት የሚፈጥረው የአቶ ገብሩ መጽሐፍ ለታሪክ የሚተወው ማስታወሻ ምን ሊሆን እንደሚችል መቃኘቱ አይከፋም። ዘመኑን ያልተረጋጋ፣ የአፈና፣ የስደት፣ የመከፋፈል፣ የመከራ፣ የእስርና የጭቆና በማድረግ ግንባር ቀደም ተዋናይ ከሆኑት ሰዎች መካከል እግዜር አንዳንዱን እየመዘዘ ቶሎ ሳይዘነጉት፣ እያደረጉ ያሉትን ነገር ቆም ብለው አስተውለው እንዲጽፉት ሲያደርግ ደስ ያሰኛል። አቶ ገብሩም በመጽሀፋቸው ደጋግመው የሚጠቀሙባት “ አሁን ቆም ብዬ ሳዬው፣ አሁን መለስ ብዬ ሳየው፣ አሁን ሳጤነው” የምትል አገላለጽ አለች። ይክፋም ይልማም ቆም ብለው የሚቆጩበት ነገር አለ ማለት ነው። ለምሳሌ በመጽሀፋቸው ገጽ 249 ላይ “አሁን ሳጤነው በአብዮታዊ ዴሞክራሲ እምነታችን ምክንያት የመረጃ ፍሰትን ገድበን የአገራችንን የአስተሳሰብ እድገት በመጎተታችንና በማጫጨታችን እጸጸታለሁ።” ብለዋል።

ይህን ያጫጩትን የአስተሳሰብ እድገት ለማምጣት ከህሊናቸው ጋር ተማምለው ፋይዳ ያለው መጽሀፍ ለማዘጋጀት መነሳታቸውን በመግቢያቸው ጽፈዋል። “ ስለሆነም ለኀሊናዬ ትክክል የመሰለኝን ሁሉ ለማስፈር ሞክሬም፣ ሰማዕታቱ የተሰውለትን ዓላማ ለማክበር ሞክሬያለሁ” (ገጽ4) በማለት ከደጋፊዎቻቸውና ተቃዋሚዎቻቸው የሚመጣባቸውን ነቀፌታ የገመቱ መስለዋል። ሚዛናዊ ነኝና ልብ አድርጉልኝ ነው ነገሩ። ቢሆንም ነቀፌታውና ውርጅብኙን ያቆሙት ዘንድ ግን አይችሉም። የሚችሉትና ችለው ያሳዩት ነገር ለታሪክ የሚሆን ማስታወሻ መተው ነው። እሱን ትተውልናል! ጥያቄው የተውልን ነገር ምንድነው? የሚለው ነው። በዚህ ዘገባ “ሉዓላዊነትና ዴሞክራሲ በኢትዮጵያ” ከሚለው ባለ 516 ገጽ መጽሐፋቸው የተውልንን ማስታወሻ ከመጠነኛ አስተያየት ጋር መቃኘት ሞክረናል። መቸም የዘንድሮ መጽሐፍ ከድንጋይ ዳቦ ዘመን ካልጀመረ፣ ታሪክ ካላስተማረ አይሆንለትም። መጀመሪያ ረጀሙና ገናናው ታሪካችንን አንስተን እንጸልይበት ካለለ ወደ ፍሬ ነገሩ መምጣት ያስቀስፋል። ስለዚህ አንዴ ሺ ዘመን አንዴ መቶ ዓመት እየሆነ እንደ ስቶክ ማርኬት ገበያ የሚወጣ የሚወርደውን ዘመን እንለፈውና ወደ አቶ ገብሩ ዘመን ቀረብ ብሎ ያለውን የመጽሐፋቸውን ገጽ ገለጥ ገለጥ እናድርገው። መጽሐፉ በስድስት ም ዕራፎች በበርካታ ን ዑስ ም ዕራፎች የተከፋፈለ በቁመቱም ዘለግ ያለ ባለ 516 ገጽ ነው። አክሱምን የድርጅታቸውን የትጥቅ ትግል ዘመን ህወሓት ለሥልጣን የበቃበትንና ከኤርትራ ጋር በመንግሥት አብሮ የኖረበትን እንዲሁም ጦርነቱንን ከጦርነቱ በኋላ ያለውን ሁኔታ ሁሉ በዝርዝር ይዳ ስ ሳል። ሰለኢትዮጵያ የዴሞክራሲና ሰብ አዊ መብቶች አያያዝ ስለምርጫን የፖለቲካ ምህዳር መስፋት መጥበብ ያነሳል። መፍትሔ ሀሳቦች ናቸው የሚላቸውንም ሰንዝሯል። እጅግ የተደከመበት መጽሐፍ መሆኑ ያስታውቃል። ከመጽሐፉ ፍሬ ነገሮች ጥቂቶቹን ለመጋራት ያህል የሚከተለው ቅኝት ተደርጋል።

ፖለቲካ ፓርቲ ተጀመረ!
geberu asrat new book
እንደ አቶ ገብሩ መጽሐፍ – ከ1930ዎቹ ቀደም ብሎ በኤርትራና በደቡብ ምስራቅ ኢትዮጵያ ትጥቅ አንግበው ከሥርዓት ጋር መፋለም የጀመሩ ግንባሮች ነበር። እነዚህ ከማዕከሉ ርቀው ይንቀሳቀሱ የነበሩ ቢሆንም ወደኋላው ላይ በአዲስ አበባ ጭምር እየተጧጧፉ ለመጡት አገር አቀፍና ብሔር ተኮር ድርጅቶች እንዲሁም የተማሪ ቤት የፖለቲካ እንቅስቃሴዎች ምክንያት ሆነዋል። በመሆኑም ከኤርትራና ከሶማልያ ድርጅቶች ቀጥሎ በ1960 በጀርመን ሃምቡርግ ከተማ በእነ ኃይሌ ፊዳ የተመሠረተው “የመላው ኢትዮጵያ ሶሻሊስት ንቅናቄ” /መኢሶን/ አንጋፋው ፓርቲ ነው። ይሁን እንጂ አቶ ገብሩ ይህን ያገኙት ተስፋዬ መኮንን በ1985 ይድረስ ለባለ ታሪኩ በሚል ርዕስ ካሳተሙት መጽሐፍ ገጽ 119 ላይ መሆኑን ጠቅሰው “አንዳንዶች መኢሶን በ1960 መመስረቱን እንደሚጠራጠሩ” ገልጸዋል። ለታሪክ በተውት መጽሐፋቸው የዘገቡት ግን “መረጃው ትክክል ነው ብለን ከተቀበልነው” (ገጽ35) በሚል ጥርጣሬ ነው። የ66 አብዮቱ ከመፈንዳቱ 10 ዓመት በፊት መሆኑ ነው።

በ1964 በጀርመን በርሊን በእነ አቶ ብረሃነ መስቀል ረዳ፣ ኢያሱ ዓለማየሁ ዘርኡ ክሸን ተስፋይ ደበሳይ የተቋቋመው የኢትዮጵያ ሕዝቦች አርነት ድርጅት / ኢሕአድ/ ኋላም አገር ቤት ከነበሩት እንደ አብዮት የመሳሰሉ ቅድመ ፓርቲ ድርጅቶች ጋር አብሮ ሲሰራ ቆይቶ መዋሃዱንና የኢትዮጵያ ሕዝባዊ አብዮታዊ ፓርቲ/ ኢሕአፓ ተብሎ መሰየሙን ተመሳሳይ ምንጭ ጠቅሰው ጽፈዋል። ከእነዚህ የህብረ ብሔር ከሆኑት የመኢሶንና የኢሕአፓ ፓርቲዎች ቀጥሎ ምናልባትም ቀደም ብለው ሌሎች የብሔር ድርጅቶች እየተቋቋሙ መምጣታቸውን ጽፈዋል። ቀደም ሲል በሜጫና ቱለማ የመረዳጃ እድር እንቅስቃሴ ሲያደርግ የቆየው የኦሮሞ ነጻነት ግንባር /ኦነግ/ በ1966 በይፋ መቋቋሙን ዘግበዋል። ከእነዚህ ሁሉ የቀደመውና እንደ ሌሎቹ በኤርትራ ተጠልሎ ይንቀሳቀስ የነበረው የብሔር ድርጅት በ1962 በትግራይ ተወላጆች የተቋቋመውና በመምህር ዮሐንስ ተክለ ኃይማኖት “ማህበር ፖለቲካ” ተብሎ የሚጠራው ነው። የትጥቅ ትግል በማንሳት ከኤርትራ ድርጅቶች ቀጥሎ በሰሜን ኢትዮያ የተቋቋመው ግምባር ገድሊ ሓርነት ትግራይ /ግገሓት/ የትግራይ ትግሪኝ ወይም ኤር-ትግራይ በሚል ኤርትራና ትግራይን አቀናጅቶ አንድ አገር ለመፍጠር የተነሳ መሆኑ በመጽሐፉ ተጽፏል። ለማንኛውም እነዚህኞቹን ጀብሃ ኢሕአደንን ደግሞ ሻዕቢያ እየደገፉት ለትጥቅ ትግል ዝጅግት ሲያደርጉ እስከ 1967 በኤርትራ ቆይተዋል። የትጥቅ ትግል ለማድረግ በኤርትራ እየተደገፉ ከተቋቋሙ የትግራይ ብሔር ድርጅቶች መካከል ሌላኛው መጀመሪያ ማህበረ ገስገስቲ ብሔረ ትግራይ ቀጥሎም ተጋድሎ ሓርነት ህዝቢ ትግራይ /ተሓህት/ እያደርም ህወሓት ሆኖ የወጣው ድርጅት መሆኑን ከገብሩ መጽሐፍ መረዳት ይቻላል። የትግራይ ተማሪዎች ገና ዩኒቨስቲ መግባት ሳይደርሱ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት እያሉ ይቀሰቀሱ እንደነበር ገብሩ የራሳቸውን ታሪክ እያመሳከሩ እንዲህ ጽፈዋል፟-
“ገና ዘጠነኛ ክፍል እያለሁ አንዳንድ ከቀዳማዊ ኃለሥላሴ ዩኒቨርስቲ የመጡ ስለአገሪቱ ፖለቲካ ችግሮች እያነሱ ይቀሰቅሱ ነበር..በ1960ዎቹ መጀመሪያ የክልሉ ተወላጆች የሆኑ የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ክረምት ለዕረፍት እየመጡ ፖለቲካዊ ቅስቀሳዎችን ያካሂዱ ነበር።” (ገጽ 40) “የትግራይ ተወላጅ የሆኑት
የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች ለእረፍት ሲመጡ የክረምት አካዴሚያዊ ትምህርት እንሰጣለን በሚል ሽፋን የፖለቲካ ትምህርት መስጠት ጀምረው ነበር። እነዚህ አስተማሪዎች የሚሰጡን ትምህርት አብዛኛውን ጊዜ የቀዳማይ ወያኔ እንቅስቃሴን በተመለከተ ሰፊ ማብራሪያ ይሰጡን ነበር” (ገጽ 41” ብለዋል። የትግራይ ብሔርተኞች የተለያየ ስያሜና የፖለቲካ አስተሳሰብ ቢኖራቸውም ዞሮ መግቢያ መደምደሚያቸው ያቺው ትግራይነታቸው መሆኑን ለማስተዋል የአቶ ገብሩ መጽሐፍ ጥሩ የማመሳከሪያ ሰነድ ነው። ከትግራይም ደግሞ እንዲሁ ወደ ጎጥ እየወረዱ ይሄዳሉ። እነሆ የገብሩ ቃል!“በትግራይ የሚንቀሳቀሱ ድርጅቶች
ተሓትን ጨምሮ እጅግ ወግ አጥባቂ ባህል የተጠናወታቸው ነበሩ። የድርጅቶቹ አመራሮቹም ቢሆኑ ከዚህ የጸዱ አልነበሩም። እንዲያውም አንዳንዶቹ ሥር የሰደደ ኋላ ቀርነትና ጎጠኝነት የተጠናወታቸው ነበሩ።(ገጽ 82)ከፍ ሲል ያየነውና አቶ ገብሩ በመጽሀፋቸው በአንጋፋነታቸው ከጠቀሷቸው ህብረ ብሄር የፖለቲካ ድርጅቶች መኢሶን አንዱ ነበር። የዚሁ ድርጅት አመራር የነበሩት ዶ/ር ነገደ ጎበዜ ሰሞኑን “ይድረስ ከየካቲት ለግንቦት” ብለው በወቅቱ ይዋደቁ የነበሩት የኢትዮጵያ ተማሪዎች ዓላማና አደረጃጀት ምን እንደነበር ባወሱበት በዚህ መጽሐፋቸው እንዲህ ብለዋል “ በዛሬው ግርግርና የብሄር /ብሄረሰብ ድርጅቶች ማየል የተነሳ ብዙ ሰው ልብ የማይለው ቁም ነገርና እኛ መኢሶኖች የቀሰምነው ትምህርት አለ፡፡ መሬት ለአራሹ ብለን ያኔ ስንዋደቅ ለመላው የኢትዮጵያ ህዝቦች ደህንነት በአንድ ላይ ታግለን ነው፡፡ የደርግ መንግስት የመኢሶን መሪዎች በማለት በአንድ ቀን አምስት ታጋዮችንን ማለትም፤ ሀይሌ ፊዳን፤ ዶክተር ንግስት አዳነን፤ ቆንጂት ከበደን፤ ደስታ ታደሰንና ሃይሉ ገርባባን ወስዶ ሲረሽን እነዚህ መሪዎቻችን ከኦሮሞ፤ ከትግራይ፤ ከአማራና ከጉራጌ ብሄሮች የተውጣጡ ዜጎች ነበሩ፡፡ ለዚህ ወይም ለዚያ ብሄር ሳንል በአንድ መንፈስ በአንድ አላማ በወንድማማችነት መንፈስ ታግለናል፡፡”እነ አቶ ገብሩ የሞቱለት ድርጅት በራሳቸው መጽሐፍ ገጽ 43 ላይ እንደምናስተውለው ገና ከማለዳው በትግራዮቹ ታጋዮች ዘንድ “የታላቋ የኢትዮጵያ አስተሳሰብ አራማጅ” ተብለው መወጀንልና መፈራረጅ የነበረ መሆኑን ነው። የካቲት 11 ቀን 1967 ደደቢት ላይ ትጥቅ ትግል የጀመረው ተሓህት ጠመንጃ ማጮህ ጀመረው ወዴት እንደሚሄድ ምን እንደሚፈልግ አጥርቶ ሳያውቅ፣ በገብሩ አነጋገር “በሰነድ የሰፈረ የፖለቲካ ፕግራም” ሳይኖረው ነው። “ተሓህት ውስጥ እስከ 1968 ዓም ድረስ የዚህ ዓይነቱ ክፍተት ስለነበር አባላቱ የተሓህትን ዓላማ በመሰላቸው መንገድ ይገልጹት ነበር። አንዳንዶቹ የተሓህት ዓላማ የትግራይን ሕዝብ ነጻ ማውጣት ነው ሲሉ” ሌሎች ደግሞ የመደብ ትግል በማካሂያድ ጭቁኖችን ነጻ ለማውጥት ነው ይሉ ነበር። የብሔር ጥያቄና የመደብ ትልግ የተዘባረቁበትና አቅጣጫም ያጡበት ሁኔታ ነበር።”45

ከመጽሐፉ የተወሰዱ
gebru asrat
1ኛ. ህወሃት በ17ቱ የትግል ዓመታቱ 54ሺ ሰዎች መሞታቸውንና ከነዚህ 90 ከመቶ የሚሆኑት የገጠር ወጣቶች ናቸው። በገጽ 165 ።
2ኛ. “የህወሓት/ኢህአዴግ መሪዎች በሚሊዮኖች የሚገመት ገንዘብ እያፈሰሱ ህዝቡ ትግላቸውን እንደገድለ ሰማዕታት እንዲቀበለው አድርገው በሥልጣን ለመቆየትና ከሞቱም በኋላ ዘለዓላማዊ ክብርና ዝና ለማግኘት መሞክሩን ተያዘውታል። ይህን የህዝብና የሰማዕታት የተጋድሎ ታሪክ ጠቅልለው ለአንድ ሰው ለማሸከም ይሞክራሉ። ሰውየው ከሰውነት አልፎ እንዲመለክ ለማድረግ ይሞክራሉ። ይህን ሁሉ የሚያደርጉትም በአሁኑና በወደፊቱ ተግባሮቻቸው ከመኖር ይልቅ ባለፈው ታሪክ መኖሩ ለሥልጣናቸው ህልውና ጠቃሚ ሆኖ ስላገኙት ነው።(ገጽ 4)
3ኛ. እጅግ የሚያናድደኝ ይህ በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን የሚተላለፈው የዘመነ ምኒልክ የጎፌሬዎች ቀረቶና ሸለላ ነው።- ስብሀት ነጋ ገጽ 303
4ኛ. የደርግ ሠራዊት አባላት በግለሰብ ደረጃ እውቀታቸውንና ክህሎታቸውን በጥቅም ላይ የሚያውሉበትና አዲስ በተደራጀው ሠራዊት ውስጥ በአባልነት የሚቀጥሉበት ሁኔታ ቢመቻች ኖሮ ከፖለቲካው አንጻር ይፈለግ የነበረውን የብሔር ብሄረሰብ ስብጥር ከማሟላትም ሌላ የረጅም ጊዜ ልምዳቸውንና እውቀታቸውን አገራዊ ሠራዊት ለመገንባት ባዋሉት ነበር።222
5ኛ. አሁን ሳጤነው በአብዮታዊ ዴሞክራሲ እምነታችን ምክንያት የመረጃ ፍሰትን ገድበን የአገራችንን የአስተሳሰብ እድገት በመጎተታችንና በማጫጨታችን እጸጸታለሁ። ገጽ 249
6ኛ .. ኢህ አዴግ ተቃዋሚዎችን ለመድፈቅና ለማጥፋት ከሚጠቀምባቸው ስልቶች የአመራር አባላቱንና ከፍተኛ ኃላፊዎችን መቆጣጠር። በጥቅም መግዛትና መደለለል ነው። በክፍያ መዝገብ ስማቸው የሠፈረ አሁን ድረስ ተቃዋሚዎች ነን እያሉ የሚንቀሳቀሱ የማውቃቸው አሉ። የነዚህ ሰዎች ተቀጣሪነት ያወቅኹት በኢሕአዴግ አመራር አባልነቴ ሳይሆን ቅርበት ከነበረኝ የደሐኀንነት አባላት ነውና አሁንም የነዚህን የማውቃቸውን ሰዎች ስም ላለመጥቀስ መርጫለሁ። 251
7ኛ. ኢሕአዴግ አማራው ክልል ውስጥ ሲንቀሳቀስ ጠባቦች መጥተው ሊውጡህ ስለሆነ ከ እነርሱ የሚያድንህ ከኢህ አዴግ ጎን ተሰለፍ ብሎ ይቀሰቅሳል። በኦሮሚያ በትግራይና በሌሎች ክልሎች ደግሞ ትምክህተኞች ዳግም አንሰራርተው ሊውጡህ ነው ኢሕ አዴግን ካልተቀበልክና ካልደገፍክ መቀመቅ ትገባለህ እያለ በማስፈራራት ይቀሰቅሳል። ገጽ 199
8ኛ. የሓየሎም ሞት ገዳዩ ኤርትራዊ መሆኑን እያወሱ ከኤርትራ ከነበረው አለመግባባት ጋር ያያዙታል። ይህ ፍጹም ሊሆን አይችልም ብሎ ለማለትም ያዳግታል። 265
9ኛ. (ስለተባረሩ ኤርትራውያን) ጉቦ እየተሰጣቸው መባረር ያለባቸውን እያስቀሩና መባረር የሌለባቸውን ያባርሩ እንደነበር የሚባረሩት ንብረታቸውን ሲሸጡ ተደራጅተው ንብረቱን በርካሽ ይገዙ እንደነበር ኋላ ላይ ተጋልጧል።…እኛን ፀረ- ኤርትራውያንና ፀረ- ዴሞክራሲያዊ ናቸው እያሉ ሲከሱን የነበሩ ቱባ ባለሥልጣኖች ሳይቀሩ ኤርትራውያን ሲባረሩ ቪላዎቻቸውንና የንግድ ድርጅቶቻቸውን ገዝተው እንደነበር ተራው ዜጋ ሳይቀር ያውቀዋል። ሆኖም የህወሃት/ኢህአዴግ አመራር በአንዱ ወይም በሌላው ከኤርትራውያን ጋር በተያያዘ ወንጀል ተዘፍቀው ስለነበር “በመስተዋት በተሠራ ቤት የሚኖር ሰው በድንጋይ አይጫወትም” እንዲሉ ምንም ማድረግ አልቻሉም። 281

እዚህ ላይ ይህን የአቶ ገብሩን አባባል ለመፈተሽ ያህል፣ የመደብ ትግልና ጭቆናን ለመቃወም ማልደው የተነሱ እንደ ኢሕአፓና መኢሶን የመሳሰሉት ሌሎች ድርጅቶች ቀድመው በተቋቋሙበት፣ በመላው ኢትዮጵያ ተማሪዎች ለለውጥ በተነሳሱበት ሁኔታ፣ የትግራይ ልጆች ለብቻቸው ተነጥለው በረሃ ግባታቸው፣
የመደብ ትግል ሳይሆን የብሔር ፖለቲካን ማራመዳቸውን ያመለክታል። ሁለቱን ማጣመር የሚቻል እንኳ ቢሆን ሁለቱንም ያጣመረ ፕሮግራም መቅረጽ አያቅታቸውም ነበር። ግን ጨወታው ወዲህ ይመስላል። ለማንኛውም ገብሩ ራሳቸው ድርጅቱ ከተቋቋመ አንድ ዓመት በኋላ የካቲት 1968 በአመራሩ ተረቆ የጸደቀውን ማኒፊስቶ ወይም መርሐ ግብር ሲጠቅሱት እንዲህ ብለዋል “ …የአብዮታዊው ትግል ዓላማ ከባላባታዊው ሥርዓትና ከኤምፔሪያሊዝም ነጻ የሆነ የትግራይ ዴሞክራሲያዊ ሪፑብሊክ ማቋቋም ይሆናል” (ገጽ 51) እዚህ ጋር ምንም እንኳ ይህ ትግራይን ለመገንጠል ያቀደ ማኒፌስቶ በአባላቱ ዘንድ ውዝግብ ፈጥሮ ከ6 ወራት በኋላ ቢለወጥም ይህን በአረቀቁት የአመራር አባላት ውስጥ የተቋጠረውን ችግር መገንዘብና መታዘብ ይቻላል። ይህን እንኳን ሌላው ሰው ገብሩ ራሳቸው በገጽ 98 እንደሚከተለው ታዝበውታል።“በዚሁ አንደኛ ድርጅታዊ ጉባኤ ድርጅቱን ይመራ የነበረው ማዕከላዊ ኮሚቴ ባሰራጨው የፖለቲካ ፕሮግራም ያካተተውን የትግራይ ዴሞክራሲያዊ ሪፑብሊክ የማቋቋም ዓላማ አንስቶ አልተቸም።…ማን በፕሮግራሙ እንደካተተው የመለየትና ኃላፊነት የመውሰድ ድፍረቱም አልነበራቸውም….ሁሉም እኔ አልነበርኩበትም የሚል መግለጫ ሲሰጡ ይደመጣሉ።” ረቂቅ ፕሮግራሙን እንዲያዘጋጁ ድርጅቱ በወቅቱ መድቧቸው የነበሩት ሁለት ሰዎች ግን መለስ ዜናዊና አባይ ፀሐዬ መሆናቸውን ገብሩ ጽፈዋል። ይህን የማስተዋል ጥቅሙ፣ ነገር መደበቅ፣ መቅጠ ሽምጥጥ አድርጎ በግልም ሆነ በቡድን መካድ ገና ከማለዳው አብሯቸው ተወልዶ ያደገ ልማድ መሆኑን ነው። እንጂማ በፕሮግራም የተጻፈን ነገር ማን እንደጻፈው ማን እንዳዘጋጀው ሳያታወቅ ቀርቶ አይደለም። ከዚህ መጽሐፍና ከሌሎችም መረጃዎች በመነሳት ሕወሓት ማለት አመራሩ ዐይኑን በጨው አጥቦ የሚቀጥፍበት፣ አባላቱም ያዩትን እንዳላዩ ሆነው ማለፉን የተካኑበት ብሔርተኝነት ብቻ አቆራኝቷቸው ተቻችለው የሚኖሩበት
ድርጅት ነው ማለትም የሚቻልበት ሁኔታ ይታያል።

ትግራይ ባንዲራ ነበራት እንዴ?

አቶ ገብሩ ብዙ የተዋደቁለትን ድርጅት አመራሩንና ጓደኞቻቸውን ሲተቹ አንዳንዱን ማፍረጥ እንደፈሩት ቁስል ቀስ ብለው የሚነካኩት መሆኑ ቢያስታውቅም አንዳንዱን ግን ያለምህረት ይሉታል። ለምሳሌ ይህንን በመጽሐፋቸው ገጽ 100 ላይ የታዘቡትን የድርጅታቸውን ጉድና ትዝብት እንመልከት፣ “መጀመሪያ ባንዲራው ከመቀየሩ በፊት የህወሓት ባንዲራ ጥቁርና ቀይ ነበር። “ቀይ መስዋአትነት ቢጫ ተስፋ ኮከብ ዓለም አቀፋዊነት በመጀመሪያ ባንዲራው ለምን ጥቁር ቀለም ተካተተ የሚል ጥያቄ ሲቀርብም በደፈናው የድሮው ትግራይ ባንዲራ ያን ይመስል ስለነበር ነው። የሚል መልስ ይሰጥ ነበር። ኖም ተሓህት/ህወሓት ይል ከነበረው ውጭ በታሪክ ትግራይ የራሷ ባንዲራ ነበራት የሚል ማረጋገጫ አላገኘሁም።” ብለዋል። መቸም አቶ ገብሩ ያላገኙትን አንባቢዎችስ ብንሆን ከየት እናመጣዋለን!ሉዓላዊነት በሶማልያም በኩል ነበር! አቶ ገብሩ ትሑት መሆናቸው ንግግራቸውንም ትችታቸውንም በወጉ ማድረጋቸው ያስመሰግናቸዋል። አንዳንዴ አፍታተው ወይም ጠበቅ አድርገው ሀሰቱን ሀሰት እውነቱን እውነት ቢሉ ከዚያም ርቀው ምነው አንዳንድ ነገሮች ማለት በቻሉ ያሰኛል ። ብዙ ማስረጃ እየደረደሩ የሞገቱትን ሐቅ እንኳ ደፍረው እንዲህ ነው ብለው አይቋጩትም። እያደር ህብረ ብሄራዊና ለሉዓላዊነቱ የሚቆረቆር ድርጅት እየመሰለ መምጣቱን መግለጽ የሚፈለገው ድርጅታቸው በሶማልያ ወረራ ጊዜ እንደሌሎቹ ወረራውን ማውገዝ ብቻ ይሆን ከደርግ መንግሥት ጋር ተሰልፎ ለእናት አገሩ ለመዋጋት ሀሳብ የነበረው መሆኑ እንዲመዘገብለትና የክህደት ታሪኩ እንዲፋቅለት ሲጥር መኖሩ ይታወቃል። ይህን በጨርፍታ አንስተው የተቹት አቶ ገብሩ የአቶ ስብሐት ነጋን አንዲት አብነት አንስተው እንደሚከለተው ጽፈዋል፦

“የድርጅቱ ሊቀመንበር ስብሐት ነጋ ሶማልያ በኢትዮጵያ ላይ ጥቃት ስትሰነዝር ከደርግ ጋር በመሆን ጥቃቱን ለመመከት ሓሳብ አድርገን ነበር ቢልም በድርጅቱ ታቅፎ የነበረው አባል ሁሉ ይህን ዓይነት ጥሪ እንደተደረገ ፍጹም አያስታውስም። አባባሉም በሰነድ ሊደገፍ የሚችል አይደለም። ያ ቢሆን ኖሮ የተቃወሙትንና የመስፋፋት ፖሊሲውን ያደናቅፋሉ ያላቸውን የኦሮሞ ተወላጆች ያሰረውና የገደለው ዚያድ ባሬ ተሓህት/ህወሓት በሞቃዲሾ ተወካይ ኖሮት እንዲንቀሳቀስ ባልፈቀደ ነበር። የሶማልያ የይለፍ ፓስፖርት ለተሓህት/ህወሃት ባለሥልጣናት አባላት ባልሰጠ ነበር። ለተሓህት/ህወሃትን በጦር መሣሪያ ባላስታጠቀ ነበር። 93 እንዲያውም ገብሩ ይህኑ የሚያጠናክር መረጃ በሌላኛው ገጽ 117 ላይ ሰጥተዋል። “ የህወሃት ፖለቲ ቢሮው እኔና አው አውሎም ወደ ኤርትራ ሳህል ሄደን ..የሶማልያ መንግሥት የሰጠንንና በሻዕቢያ በኩል ተጓጉዞ እንዲደርሰን የተስማማንበትን ከ3ሺ በላይ ክላሺንኮቭና ሲሞኖቭ ጠመንጃዎች ከነመሰል ጥይቶቻቸው የመረከብ…ተልእኮም ሰጥቶን ነበር” እያሉ ጽፈዋል። ስለዚህ ድርጅታቸው የአገር ሉዓላዊነት ሊያሳስበው ቀርቶ ከወራሪው ኃይል ጋር ተስማምቶ መሣሪያ እስከመታጠቅ መድረሱን አጋልጠዋል። ይሁን እንጂ ሉዓላዊነትን በኤርትራ ብቻ ሳይሆን በሶማልያም በኩል አያይዘው ቢያነሱትና ቢያሰፉት መልካም ነበር። ለወረራውም ቢሆንኮ ኤርትራ እናት አገሯን ከእናት አገሯም ትግራይን ነው የወረረችው ሶማሌን ግን ጎረቤቷን ነው የወረረችው ብለው የሚያስቡ ሰዎች አሉ። ወይንም አለን።

ኤርትራን እናስተኛት!?

ከገብሩ መጽሀፍ የሉዓላዊነት ፍሬነገሮች ሁለቱን ዋና ዋና ነገሮች አውጥተን ብንመለከት አንደኛው ቁጭታቸው ሌላኛው ስጋታቸው ነው። ስለተቆጩበት እንዲህ ይላሉ-፤ “ከሁሉም በላይ የሚከነክነው በወቅቱ ኢትዮጵያ በዓሰብ ላይ የነበራትን የባለቤትነት መብት ያመለምንም ድርድር ለሻዕቢያ አሳልፋ መስጠቷና በታሪክ ትልቅ ጥቁር ነጥብ መጣሉ ነው። ከ30 ዓመት በላይ የህዝቦችን ደም ያፋሳሰሰው ጦርነት በሰላም መፈታቱ ተገቢ ቢሆንም የኢትዮጵያ ጥቅሞች ሳይከበሩ ያለምንም ቅድመ ሁኔታ በአንድ ኮንፈረንስ ለኤርትራ ነጻነት ሕጋዊ እውቅና መስጠቱ ግን ከፍተኛ ስህተት ነበር። የኮንፈረንሱ ተሳታፊዎች
ከዚህ ስህተት ተጠያቂነት ሊያመልጡ ባይችሉም ዋናው ተጠያቂ ግን ውሳኔውን የቀየሰውና ተቀብይነት እንዲያገኝ ቁልፍ ሚና የተጫወተው የህወሓት/ኢሕአዴግ አመራር ነው። (ገጽ 184)ስጋታቸው ደግሞ የኤርትራ መንግሥት መቸም አይተኛልንም የሚል ነው። “ ..እንደኔ አመለካከት በኢሳያስ የሚመራው
የሻዕቢያ መንግሥት ኢትዮጵያን ለመውረር ያነሳሳውን በአካባቢው የኢኮኖሚ፣ የወታደራዊና የዲፕሎማስያዊ የበላይነት የመጎናጸፍ ፍላጎት እስካሁና አልጠፋም።..ኢትዮጵያን በማዳከምና በመበታተን በአካባቢው የበላይ የሚሆንበትን ስትራቴጂ ቀይሶ በመንቀሳቀስ ከትግራይ ጀምሮ እስከ ኦጋዴን ትግል እያካሄድን ነው ብለው ለሚያምኑ….መጠጊያ ሆኖ ሥልጠናና ትጥቅ በመስጠት ኢትዮጵያን ለማተራመስ እየሠራ ነው፡፡ (ገጽ 427)
geberu asrat new book
እነዚህን የአቶ ገብሩ ሁለት ቁጭትና ስጋት ፈጣሪ ነገሮችን ብንመለከት። አንደኛ የፈሰሰ የቀይ ባህር ውሃ አይታፈስም። ጥፋተኞችን ለፍርድ ማቅረብም ቢሆን አገርና ዘመን ላይ አይፈረድም። በታሪክ ተጠያቂ የሚባለውም ነገር ታሪክ ማንን ጠይቆ እንዳፋጠጠ ስላማናውቅ ብዙ አንራቀቅበትም። እንኳን ሊያፋጥጣቸው ይኸው ታሪክ ሰሪዎቹ በቁማቸው መጽሀፍ እየጻፉ በቁማችን ያስነበቡናል። ኤርትራ ትወረናለች አትተኛልንም ማለቱም ጥሩ ስጋት ነው። ታዲያ እንድትተኛልን ምን ማድረግ ይበጃል? ኤርትራ ኢትዮጵያን መጥላት ትታ ራሷን ብቻ ብትወድ ኖሮ ይኼኔ የት በደረሰች ብሎ መምከር ይቻል ይሆናል። ግን ትግሬ ለአማራው፣ አማራው ለትግሬ፣ ኦሮሞው ለአማራ፣ አማራው ለኦሮሞው፣ እስካልተኙ ድረስ እኛም ለኤርትራ ኤርትራም ለኛ ትተኛለች ብሎ መጠበቅ አይሆንልንም። መቸም በዚሁ ገመድ ሲጠላለፉና ሲገዳደሉ የኖሩት ምሁራኑ ፖለቲከኞቻችን ይህን አፍታተው የሚያውቁት ጉዳይ ሊሆን
ይችላል። ይልቁንስ መበላላት የትም ካልቀረ ኤርትራውያን ተመልሰው መጥተው እዚሁ ከኛው ጋር እየተበላሉ ቢኖሩ ይሻላቸዋል ብሎ ከመቀለድ ጋር ቁጭት የሚፈውሰውን ስጋት የሚያስቀረውን ዘለቄታዊ መፍትሔ ማሰቡና ስለሱ መጻፉ ይበጃል።

የአቶ ገብሩ መጽሀፍ ጉልበቱ አንባቢን እስከዚህ ድረስ በሀሳብ መንዳቱ ነው። የሚያሳስበው ትልቁ ነገር የኤርትራ ጉዳይ የውስጥ ጉዳይ ሆኖ ይዝለቅ ወይስ እዚያው እየተገፋ ከባህር ይጥለቅ የሚለው ጥያቄ ነው። ቀኝ እጁ ኢትዮጵያዊ ግራ እጁ ኤርትራዊ እየሆነበት ግራ የተጋባ ትውልድ፣ አንዴ እንጣበቅ አንዴ እንላቀቅ፣ ከሚል ማለቂያ አልባ ፍልሚያ የሚገላገልበት መካሪ መጽሀፍ ማስፈለጉን የገብሩ መጽሐፍ ሹክ ይላል። ካለበለዚያ መሬት ወንበር የሆነ ይመስል እስኪ እሱን የተቀመጥክበትን መሬት አቀበልኝ አይባልም። ስለዚህ ይህን ችግር አሰብ፣ ወደብ፣ ባድመ፣ ሉዓላዊነት፣ የሚል ጥያቄ ብቻውን አይፈታውም። ከወንድማማቾች ጋር ዘላቂ ሰላም የሚመጣው፣ መሬት በመተሳሰብ ሳይሆን፣ እርስ በርስ በመተሳሰብ ነው። እሱን ደግሞ ስላቃተን ነው ወንድም ወንድሙን ወግቶ ድል ሊነሳ በረሃ የሚወርደው። በእነ አቶ ገብሩ መጽሐፍ የሚታየውም ይኸው ነው። ማንኛቸው ኢትዮጵያዊ ማንኛቸው ኤርትራዊ መሆናቸውን መለየት እስኪያቅታቸው ድረስ እንደቆቅ ሲጠባበቁና ሲተናነቁ ኖረው መጨረሻቸውና መጨረሻችን እንዲህ ሆኖ ቀርቷል። አቶ ገብሩ እንደሚነግሩን በድርጅታቸው ህወሃት የትግል ዘመን የሞቱት የትግራይ ልጆች ብዛት ወደ 54ሺ ይጠጋል። ይሄ ቁጥር ባንድ ሰሞኑ የባድመ ጦርነት ብቻ ካለቁት 70 እና 80ሺ ሰዎች ቁጥር ጋር ሲተያይ በራሱ የሚናገረው ነገር ይኖረዋል። የሚሰማው ከተገኘ! ለማንኛውም አቶ ገበሩ የድንበር ማካለልንና የአልጀርስ ስምምነትን አለመቀበልንና ኢትዮጵያ የባህር በር ባለቤትነቷን የምታረጋግጥበትን መንገድ የመሻት አስፈላጊነትን በመፍትሔነት ከዘረዘሯቸው ሀሳቦች ውስጥ ይካተታሉ። ይህ ሁሉ የሁለቱ አገሮች ግንኙነት በዚሁ ይቀራል ኤርትራም እንደወጣች ትቀራለች፣ ወይም እንደ አንዳንዶቹም የታባቷንስና በዚያው መቅረት አለባት ከሚል ስጋትና ፍላጎት የመነጨ ይመስላል። ያም ሆኖ ግን ገብሩ ምንም እንኳ ትልቁ ተስፋ ሰጪ ነገር አድርገው ባያጎሉትም በገጽ 478 ላይ በመፍትሄነት ከዘረዘሯቸውና በመጨረሻውና በ4ኛ ደረጃ ባሰፈሩት ላይ፣ “ሁለቱ አገሮች የላቀ የፖለቲካና የኢኮኖሚ ትስስር ለማድረግ ከተስማሙ፣ ህዝቡን በስፋት ያሳተፈና የቆየውን ባላንጣነት የሚያስወግድ ግንኙነት እንዲመሠርቱ ህዝቦቻቸው በነጻ የሚገናኙበት ሁኔታ መመቻቸት አለበት” ብለዋል። የህዝብ ለህዝቡ ግኑኝነት መሻሻል (ኖርማይላዜሽን) በሰከነ መርሃ ግብር ተደግፎ ወደላቀ ትስስር ለማምራት በር ከፋች መሆን እንዳለበት አሳስበዋል። በአቶ መለስ ወገኖችና በእነ አቶ ገብሩ ወገኖች በኩል የነበረው አንዱ ፈተና ይሄን የህዝብ ለህዝብ ሚዛን የመጠበቅ ችግር መሆኑንም ከጠቅላላው የአቶ ገብሩ መጽሀፍ ይዘት መረዳት ይቻላል። ሻዕቢያና ወያኔ ተብለው ትግራይ ትግሪኝ ሆነው አብረው ለአንድ ዓላማ ለሞቱት ሰዎች ቀላል ያልሆነው ኖርማላይዜሽን ለሌላው ሊከብድ መቻሉንም ከመመርመር ጋር፣ ይህን ሀሳብ ከመደገፍ የተሻለ ሌላ አማራጭ ያለ አይመስልም። በመጽሐፍ የተዘረዘሩት ሌሉቹ የአቶ ገበሩ አማራጮችም ከዚህኛው ጋር ባይሻሙ ይሻላቸው ነበር።

ወያኔን አትናገሩ ህወሓትን ግን እንደፈለጋችሁ!

ማለት የፈለጉትን አይበሉት ወይም ካሉት በላይ አይግለጹት እንጂ አቶ ገብሩ አስራት በተዋቃሚው ጎራ የሚታመሙበት አባባል ያላቸው ይመስላል። የምርጫ 97ን ወቅት እያሰቡ እንዲህ ጽፈዋል “የወቅቱ ተቃዋሚዎች የትግራይን ህዝብና ህወሓትን ያለመየት ችግር የሚጀምረው ከህወሓት ስያሜያቸው ነበር። ምንም እንኳን ህወሃት “ህዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ ተብሎ ቢጠራም ተቃዋሚዎች ህወሃትን የሚጠሩት ወያኔ ብለው ነበር። ወያኔና ህወሃት አንድ አይደሉም። ወያኔ በትግራይ ህዝብ ሥነ-ልቦና ከፍተኛ ቦታ ያለው የአልገዛምና የእምቢተኝነት መገለጫ ነው። ህወሓትም ይህን ስያሜ የመረጠው የህዝቡን የቆየ ሥነ-ልቦና ለማጋራት ነው።” ወረድ ብለውም “ኢህአዴግ ራሱ በፈጠረውና አንዳንድ ተቃዋሚዎችም ባስተጋቡት የፍርሃት ድባብ ምክንያት ብዙ የትግራይ ተወላጆች በገዛ አገራቸው በስጋት እንዲኖሩና አማራጭ አጥተው የኢህአዴግን ከለላ እንዲሹ አድርጓቸዋል። ለህወሓት/ኢህአዴግ አንዱ የሥልጣን መሠረት
የሆነውም የእነዚህ በስጋት የተዋጡ ዜጎች ሥነ-ልቦና ነው።” (ገጽ 436)አቶ ገብሩ ይህን ይበሉ እንጂ በድርጅታቸውም በኩል ያለውንም የተጠያቂነት ችግርና ድርሻ አልዘነጉትም። ምክንያቱም ቀደም ሲል በመጽሐፋቸው በገጽ 140 ላይ የሚከተለውን ጽፈዋል “ የጠባብነት ጥያቄ ከተነሳ መጠየቅ የነበረበት
ከጅምሩ ብሔራዊ (ትግራዊነት?) ስሜትን ከአገራዊ አንድነትና ስሜት በላይ በማስጮኽ ይቀሰቀስ የነበረው አመራሩ ነበር። ድርጅቱ (ህወሃት) ከሌሎች አገር አቀፍና ብሔር ተኮር ድርጅቶችጋ ያደረገው ትስስር ደካማ ነበር። እንዲያውም ከመሸ በኋላ ከኢሕዴን ጋር ከፈጠረው ግንባር ውጪ፣ ለአስራ ሶስት ዓመታት ያህል በብሄር ተደራጅቶ በተናጠል የተጓዘበት ሁኔታ ነበር። የላብ አደሩ ፓርቲ ሲመሰረት እንኳን ብሔር ተኮር መልክ ይዞ (ትግራይ ብቻ ሆኖ?) እንዲደራጅ ተደርጓል፡፤ እነዚህ በአመራሩ የተቀየሱ ዓላማዎች አደረጃጀቶችና የትግል ስልቶች በታጋዩ ሥነ-ልቦናና አስተሳሰብ ላይ ተጽእኖ ነበራቸው። የታጋዩ አስተሳሰብ ቅድሚያ ተሰጥቶት የተገነባበት አቅጣጫ በብሔራዊ ወይም ክልላዊ ማንነቱ እንጂ በኢትዮጵያዊ ማንነቱ ዙሪያ አልነበረም። በአጠቃላይ የተከተልነው የትግል ስልት ዋና ማጠንጠኛም ብሄራዊ እንጂ አገራዊ ወይም መደባዊ አልነበረም” በወዲያና ወዲህኞቻችን ምህረት አልባ ነቀፋ አጣብቂኝ ውስጥ ያሉት ገብሩ ይህን ሲሉ በፍጹም ቅንነት የተናገሩት መሆኑን ያለጥርጥር መገመት ይቻላል። አቶ ገብሩ በዚህ መጽሐፋቸው ያወቁትን ሁሉ ተናግረዋል ማለቱ ጨርሶ የማይታሰብ ቢሆንም ሆን ብለው ያጣመሙት ነገር አለ ብሎ ለማሰብም ይቸግራል። የሚያግባባ ነገር ላይጽፉ ይችላሉ የጻፉት ግን ያመኑበትን ነው ብሎ ማሰቡን መጽሐፋቸው አይከለክልም።

ሉዓላዊነት እና ባለማህተቡ ኢህአፓ

ምንም እንኳ የድርሻቸውን ያህል ስህተትና ተጠያቂነትን የሚጋሩ ቢሆንም፣ ምንም እንኳ አብረዋቸው በእምነት ተሳፍረው እንድ ዓለም ሰፍተው እንደመንደር ጠበው፣ በክህደት የተንጠባጠቡ ቢኖሩባቸውም፣ ምንም እንኳ የእድሜና የርዕዮተ ዓለም ለጋነት እናም የዋህነት ለቅጽበት አሳስቶ የፈጃቸው ቢመስልም፣ በእናት አገር ኢትዮጵያ ፍቅር ግን ስተው ያልተገኙት የኢህአፓ ልጆች ታሪክ እያደር ይፈካል። እንደ ስልባቦት ከላያቸው የሚገፈፈው ስህተታቸው ሲነሳ እንደ ወተት የነጣው የልጅነት ልባቸው ወከክ ብሎ ይታያል። ያን ጊዜ ገድላቸው እንኳን በወዳጆቻቸው የኛ ልጆች አይደላችሁም ብለው በፈጇቸው ጠላቶቻቸው አንደበት ጭምር ይመሰከርላቸዋል። ኢህአፓዎች ሥርዓትን እንጂ አገራቸውን አለመክሰሳቸው ለሌሎች ሁሉ እንጂ ለራሳቸው ወገን ብቻ ያልሞቱ የማንነት ስግብግቦች አለመሆናቸውን እነሆ ታሪክ ይናገርላቸዋል። በገዛ ግዛቱ እንደ ውጭ ጠላት እያሳደደ በወጋቸው፣ በቀድሞው የህዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ ድርጅት፣ ፖሊት ቢሮ አባልና አንጋፋ ታጋይ አቶ ገበሩ አስራት ብዕር ሳይቀር እንደሚከተለው ተመስክሮላቸዋል!“ኢህአፓ በአብዛኛው የመኻል አገር ከተሞች በምሁራንና በወጣቶች ከፍተኛ ድጋፍ የነበረው ፓርቲ ቢሆንም በብሔር ድርጅቶች ዘንድ ተቀባይነት አልነበረውም። በተለይ ተሓትና ኦነግ የብሔር ብሔረሰብ አቋሞቹን በተመለከት በጥርጣሬ ይመለከቱት ነበር። …..ኢህአፓ በመርህ በደረጃ የብሔር ብሔረሰቦችን መብት እስከመገንጠል ተቀብሎ ከብሔሮች ትግል ይልቅ ለመደባዊ ትግል ቅድሚያ መስጠት ይኖርበታል በማለቱና በኤርትራ ጥያቄ ቁርጥ ያለ አቋም ባለመውሰዱ በአንዳንድ ብሔር ተኮር ድርጅቶች በተለይ ደግሞ በተሓትና በሻዕቢያ የታላቋ ኢትዮጵያ (ግሬተር ኢትዮጵያ) አቀንቃኝ ወይም የንኡስ ከበርቴ ትምክህተኛ ፓርቲ የሚል ስም አሰጥቶታል። (አረጋዊ በርሔም በመጽሐፋቸው ገጽ 119 ያሉትን መጥቀሳቸውን ጠቅሰዋል)ገጽ 53። “ኢህአፓ በፕሮግራሙ ውስጥ የኤርትራ ጥያቄ በሰለማዊ መንገድ መፈታት እንዳለበት ከመግለጹም በላይ በዲሞክራሲያ በሚያወጣቸው መግለጫዎች ከሰላማዊ ድርድር ውጭ ሌላ መፍትሔ ማፈላለግ እልቂት እንጂ ሌላ ውጤት እንደማይኖረው በተደጋጋሚ ይገልጽ ነበር። ይህ የኢህአፓ አቋም የኤርትራን ድርጅቶች የሚያረካ አልነበረም። የኤርትራ ድርጅቶች
ኢሕአፓ በሁለት ጉዳዩች ላይ ጠንከር ያለ አቋም እንዲኖረው ይፈልጉ ነበር። አንደኛው አቋም የኤርትራ ጥያቄ የቅኝ ግዛት መሆኑንና ቅኝ ገዢዋም ኢትዮጵያ እንደሆነች መቀበል ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ ጥያቄው በኤርትራ ነጻነት መፈታት እንዳለበት መቀበል ነበር። እነዚህ ሁለት አቋሞች ከኢህአፓ ሊገኙ ባለመቻላቸው የኤርትራ ድርጅቶች በኢሕአፓ ላይ ከፍተኛ ጥርጣሬና ጥላቻ ነበራቸው። የኢህአፓ አቋም ባይዋጥላቸውም ኢህአፓ ደርግን ከማዳከም አንጻር ሊኖረው ከሚችለው አስተዋጽ ኦንጻር ድጋፋቸውን ይሰጡት ነበር። (ገጽ 54)
ሻእቢያዎቹ ይሰጡ ነበር የተባለውም ድጋፍ ወዲያ ተቋርጦ እንዲያውም ህወሃት ኢሕአፓን ወግቶ ሲያጠፋው እንደ ገብሩ አገላለጽ “ ሻዕቢያ አስተያየት ባለመስጠት የዝምታ ድጋፉን ሰጥትቶታል። ኢሕአፓ የኤርትራ ጥያቄ የቅኝ ግዛት ነው አፈታቱም በነጻነት መሆን አለበት፣ ብሎ ቁርጥ ያለ አቋም ባለመውሰዱ እሳት ሲጎርስ በአንጻሩ የሚፈልገውን አቋም ለወሰደው ህወሓት በመሪዎቹ በእነ ሮመዳን መሐመድ ኑርና በኢሳያስ አፈወርቂ አማካይነት ከፍተኛ ምስጋና ችረውታል። ከዚያ ጊዜ ጀምሮ ከኢሕአፓ ይልቅ ከህወሓት ጋር የተሻለ ግንኙነት ነበራቸው። (ገጽ 105) የኢህአፓ የወቅቱ ተቀናቃኝና የፖለቲካ ባላንጣ እንደነበረ የሚነገረው መኢሶን አመራር የነበሩት ዶ/ር ነገደ ጎበዜም በበኩላቸው በአዲሱ መጽሐፋቸው “ኢህአፓን ጨምሮ የየካቲት ሃይሎች እንደንጉሱ ዘመን አንዱን ወገን ብቻ እያወገዙ ከመቀጠልይልቅ የሁለቱምተጠያቂነትብቻ ሳይሆን የኤርትራ ግንባሮች በጠባብ አጀንዳ ተሰማርተው ከኤርትራም ከኢትዮጵያም ህዝቦች የጋራ ጠላቶች ጎን መሰለፋቸውን” ወደ ማውገዝ ተሸጋግረዋል ሲሉ የወቅቱን ሁኔታ ጽፈዋል። ኢትዮጵያውያን ሁልጊዜም መንግስታቸውንና ሥርዓቱን ለመቃወም ሲሉ የውጭ መንግሥታትን እርዳታ ይሹ ይሆናል። በ ኢትዮጵያዊነታቸው ግን አይደራደሩም። ሉዓላዊነት ማለት
እሱ ማለት ከሆነ በጣልያንም በሶማሌም በሻዕቢያም ዘመን ኢትዮጵያውያን ሲያከብሩትና ሲሞቱለት የኖሩት ጉዳይ ነው።

አሳሩ ገና ነው! መቸም እኛ ከገብሩ አናውቅም
የህወሃት ሰዎችም ደጋፊዎችም በኤርትራ ጥያቄና ወዳጅነት ላይ ሌላውን ሲከሱም ሆነ ሲወቅሱ ሲደመጥ መኖራቸው ይታወቃል። እሱስ ይቅር መቸም ፖለቲካቸው እንደሱ ነው። ወቀሳቸው ግን ኤርትራውያንን በፀረ ኤርትራዊነት እስከመክሰስ ከሄደ ምን ይባላል? ሉዓላዊነትና ዴሞክራሲ በኢትዮጵያ የሚለው የአቶ ገብሩ አስራት መጽሐፍ ከገጽ 125 እስከ 126 ያስፈረውን አንዲት አንቀጽ ቀንጭበን እንመልከት! በ1970ዎቹ መጀመሪያ ላይ የኤርትራ ድርጅቶች ከደርግ ጋር ሊደራደሩ ነው የሚል ጭምጭምታ በተሰማበት ወቅት ህወሃቶች እጅግ ተናደን ነበር። በአንድ በኩል ሻዕቢያ ተስፋ ቆርጦ ትግሉን አቋርጦ
እጁን ለደርግ ሊሰጥ ነው የሚል ስጋት ነበር፣ በሌላ በኩል ደግሞ ሻዕቢያ በኤርትራ ነጻነት ጉዳይ ላይ ከደርግ ጋር ሊደራደር ነው የሚል ስጋት ነበር። ሁለተኛው ስጋት አግባብ አልነበረም፡፡ …ከባለቤቱ ያወቀ ቡዳ ነው እንዲሉ ባለቤቶቹ ችግራችንን በአንድነት ማዕቀፍ እንፈታለን ሲሉ፣ እኛ የለም ይህን መሆን የለበትም ብንል፣ የድርጅቶቹን ነጻነት ከመጻረራችን ባሻገር፣ የኢትዮጵያን ጥቅም እየጎዳን እንደነበር አልተገነዘብነውም ነበር። ከዚህ በመነሳት ሻዕቢያ ከደርግ ጋር ሊደራደር ነው የሚለውን ወሬ ስንሰማ ሻዕቢያን በተምበርካኪነት ፈርጀን መክሰስ ጀመርን። የኤርትራ ነጻነት እርግፍ አድርጎ ትቶ ከደርግ ጋር ሊታረቅ እንደሚችል ገመትን። የደርግና የሻዕቢያ ጌቶችም ሶቭዬቶች ስለሆኑ ሊያስታርቋቸው ይችላሉ የሚል ግምት ስለነበረንም ስለ ኤርትራ የምንጽፋቸው ጽሑፎችና የምናወጣቸው መግለጫዎች ሁሉ የኤርትራ ህዝብ ከነጻነት ባሻገር ሌላ መፍትሔው እንዳይቀበል የሚሰብኩ ነበሩ። እንዲያውም አንዳንድ የምናወጣቸው ጽሑፎች ከኢትዮጵያ ሳይሆን ከኤርትራ ድርጅት የመነጩ ይመስሉ ነበር።

ህወሓት ኤርትራን በተመለከት ካቀረባቸው ጽሑፎች አንዱ “ብረት ህዝቢ ኤርትራ ቁልቁል አፉ አይድፋእን!” “የኤርትራ ጠመንጃ አፈሙዝ ቁልቁል አይዘቀዘቅም!” በሚል ርዕስ የተጻፈው ነበር። ይህ በመለስ ዜናዊ የተጻፈው ጽሑፍ ምሁሩና አርቆ አሳቢው ኤርትራዊው ተስፋ ጽዮን መድኃኔ ለጻፈው የተሰጠ ምላሽ ነበር፡፡…ባለቤቶቹ ጉዳዩ ሳያሳስባቸው ህወሃት ተቆርቋሪ ሆኖ መቅረቡ ያስገርማል። ኤርትራዊ ስለ አንድነትን ሲጽፍ አንድነትም ለሁለቱም ህዝቦች የሚጠቅም ሆኖ ሳለ፤ መገንጠልን ደግፈን ያን ያህል ርቀን መሄድ ባልንበረብን ጉዳዩም ይበልጥ ለኤርትራውያን መተው ነበረብን። 126 አቶ ገብሩ በመጽሀፋቸው ከቀድሞ የትግል ጓዶቻቸው ያለ ይቅርታ የሚወቅሷቸውና አውራ ተጠያቂ የሚያደርጓቸው ሟቹን አቶ መለስ ዜናዊና አቶ ስብሐት ነጋን ነው። በተለይ እጅጉን በተማረሩበትና የመጽሐፋቸውም ርዕስና ማጠንጠኛ ያደረጉት የኤርትራ ጥያቄና የሉዓላዊነት ጉዳይ ዋነኛ ተጠያቂዎቹ እነዚህ ሁለት ሰዎች
ናቸው። አቶ ሥዩም መስፍን፣ ብረሃነ ገ/ክርስቶስ ኤታማዦር ሹሙ ሳሞራ የኑስ፣ ሟቹ የቀድሞ ደህንነት ሹሙ አቶ ክንፈ ገመድህንና የአሁኑ ደህንነት ሹም አቶ ጌታቸው አሰፋ እንዲሁም የአቶ መለስ አማካሪ የነበሩ አቶ ሙልጌታ ዓለምሰገድን በተለያዩ ጊዜያት ኤርትራን አስመልክቶ በወሰዷቸው አቋሞቻቸውና ባሳዩት ተባባሪነት ታሪክ እንዲወቅሳቸው ያጠቆሯቸው ይመስላል። የስብሀትና የአቶ መለስ ግን የተለየ ነው።

ሻዕቢያዎቹ ከህወሓቶች ሁሉ አጥብቀው የሚወዷቸውና የሚያምኗቸው አቶ ስብሐት ነጋን መሆኑን ገብሩ ጽፈዋል። እንዲያውም ባንድ ወቅት ኢሳያስ ሞቅ ብሏቸው “ ስብሐት ነጋ ስልጣኑን ሳይለቅ አጥብቆ ቢሄድ ኖሮ የሻዕቢያና በሕወሃት መካከል አለመግባባት እንደማይፈጠር “መናገራቸውን በገጽ 223 ጽፈዋል። ስብሐት “ ከድርጅቱ የጸጥታ ክፍል /ሐለዋ ወያነ/ ጋር በመሆን ቀውስ ፈጣሪዎች በተባሉት ላይ የምርመራና የማጣራት ሥራ ሲያካሂድና አብዛኛውን ጊዜ የቅጣት ውሳኔ ሲሰጥ የነበረ የአመራር አባል ነበር።101” ያሉት ገብሩ ስብሐት በዚያ ልምዳቸው የተነሳ የራሳቸውን ሥልጣን ሲክቡና ሰዎቻቸውን ቦታ ቦታ ሲያዙ መኖራቸውን ይገልጻሉ። የኤርትራን ጉዳይን በሚመለከትም ስብሐት በገዛ ፍቃዳቸው መሬት አሳልፎ ይሰጡ እንደነበር እንዲህ ሲሉ ጽፈዋል። “በ1990 ዓም ግጭቶች የተኪያዱባቸውን አንዳንድ የምዕራብ ትግራይ አካባቢዎች ስብሐት ነጋ በሊቀመንበርነት ሥልጣኑ ከህዝቡ ፍላጎት ውጭ ከ1974 እስከ 1976 ባለው ጊዜ ለሻዕቢያ የሸለማቸው ነበሩ። ስብሓት መንደሮቹን ለሻዕቢያ አሳልፎ ሲሰጥ ከህወሃት የህዝብ አደረጃጀት አባላት ከፍተኛ ተቃውሞ ቢገጥመውም ማዕከላዊ ኮሚቴው ግን ለጉዳዩ እምብዛም ትኩረት አልሰጠውም ነበር።” 109አይ መለስ ዜናዊአቶ ገብሩ በጣም ሚወቅሷቸውን አቶ መለስ ዜናዊን ደግሞ እንዲህ ገልጸዋቸዋል “መለስ በወታደራዊና በሕዝብ አደረጃጀት እንቅስቃሴዎች ይህ ነው የሚባል ሚና ባይጫወትም ታጋዮችን በመቀስቀስና በመስበክ ጽሑፎችን ቶሎ በማንበብና በመጻፍ ረገድ ከፍተኛ ችሎታ ነበረው። ዐልፎ ዐልፎም ድንጋይ ዳቦ ነው ብሎ እስከማሳመን ይደርስ ነበር። አብዛኛው ገበሬና ዝቅተኛ የትምህርት ደረጃ የነበረው የድርጅቱ አባል በመለስ የስብከት ችሎታ እጅግ ይገረም ነበር። ይህ በአብዛኛው የድርጅቱ አባላት ተሰሚነት እንዲያገኝ ረድቶታትል፡፤ በ1969 ዓም ከጦርነት አፈግፍጓል ተብሎ በደረሰበት ብርቱ ሂስ ሞራሉ ዝቅ ብሎ የነበረውም መለስ ከሁለተኛው ድርጅታዊ ጉባኤ በኋላ ሲያንሰራራና የሐሳብ መሪነት ለመጨበጥ ሙከራ ሲያደርግ ታይቷል።113ሌሎች አቶ መለስን እንዴት እንደሚያይዋቸው ሲጽፉም “አረጋዊ በርሄና ግደይ ዘርአ ፅዮን መለስን ጽናት እንደሌለው ከመጠን በላይ ተናጋሪና ተግባር ላይ እንደማይገኝ ታጋይ ያዩት ነበር114” ብለዋል። ይሁን እንጂ አቶ መለስ ዜናዊ ገና ከጧቱ በሥራ አጋጣሚ ከተቀራረቧቸው “እነ ተወልደ ወ/ማርያምን ስዬ አብርሃን፣ ክንፈ ገ/መድህን ሳሞራ የኑስ ጋር የጠበቀ ዝምድና መስረታቸውንና ወደ ሥልጣን መፈናጠጣቸውን ጽፈዋል።

በመለስ ተወጥረው በተያዙበት የኢትዮ-ኤርትራ አንድ ስብሰባ ላይ የቀድሞ አቋማቸውን ሽምጥጥ አድርገው ሲክዱ አቶ ስዬ ንዴታቸውን መቆጣጠር ያቅታቸዋል ። በቃለ ጉባኤ የተያዘ ነገር እንዴት ይክዳሉ? መለስ ይቺን አጥተዋት አይደለም። ገብሩ እንዲህ ጽፈውታል- ስዬ “መለስ የቀድሞ ሐሳቡን
ለውጦ ሌላ ሐሳብ እያቀረበ እያጭበረበረ ነው፣ ይህ አኪያሄዱ ትክክል አይደለም፣ የአቋም መንሸራተቱን ለማረጋገጥ በቃለ ጉባኤው የሰፈረው ይታይልኝ ብሎ አለ። ….ቃለ ጉባኤው ቢታይ በአግባቡ ያልተመዘገበ ሆኖ ተገኘ። ምክንያቱም ቃለ ጉባኤ ያዡ በረከት ስለነበር አልመዘገበውም።” (ገጽ 340) መለስ ምናቸው ሞኝ ነው። እነ በረከትን ቃለ ጉባኤ እያስያዙ ካልሆነ እነዚህን ሰዎች የት ይችሏቸዋል። መቸም ተንኮለኛ ናቸው ። ተቃናቃኛቸው ስዬን በልማት ስም ከመከላከያ ሚኒስትርነት አንስተው የኤፍረት ስራ አስኪያጅ ሲያደርጓቸው ማዕከላዊ ኮሚቴ ብዙም ያላስታውለው ጉዳይ ነበር ይላል
የገብሩ መጽሐፍ። ለነገሩ ስመ ገናና የመሰሉት ስዬም ከዚህ ተነስተህ እዚያ ሂድ ከዚያ ወደዚህ ና ሲባሉ ዝምብለው የሚሽከርከሩ ኖረዋል እንዴ ያስብላል።መለስ ግምገማና ስብሰባ የሚወዱትን ጓደኞቻቸውን በስብሰባ እያጠመዱ እሳቸው በጎን ሥራቸውን ይሠሩ ነበር። ይህም ሌላው ጮሌነታቸው ነበር “ የሥራ አስፈጻሚውንና ማዕከላዊ ኮሚቴውን በማያባራ ውይይት ጠምዶ ዋነኛ የሥልጣን ማስጠበቂያ መሣሪያዎች የሆኑትን የጸጥታና የመከላከያ ኃይሎችን እያባባለ ድጋፋቸውን ለማሰባሰብ እየተቀንሳቀሰ እንደነበር መገንዘቡም ከባድ አልነበረም። (ገጽ 340)

መለስ ጮሌ ብቻ ሳይሆኑ ለሥልጣናቸው ሲሉ የማይፈነቅሉት ድንጋይ የማይክዱት ነገር የለም። ሌላው ቀርቶ ለሥልጣን ያበቃቸውን የትግራይ ህዝብና ጓደኞቻቸውን እንኳ አሳልፈው ከመስጠት አልተመለሱም። አጣብቂኝ ውስጥ ገብተው ከሥልጣናቸው ሊባረሩ በደረሱበት አንድ ወቅት ድርጅታቸውን ህወሃትን ትተው የአማራው ወኪሎች ነን የሚሉ ብአዴኖችን ተቀላቅለው እንዴት ከጎናቸው እንዳሰለፏቸውና ህወሓቶችን ክስ እንደመሰረቱባቸው ይታያል። ነገሩ ሲወራ የቆየ ቢሆንም ገብሩም በዚህ መጽሐፋቸው አረጋግጠውታል። አዲሱ ለገሠ እነዚህ ሰዎች (እኛን) ጠባቦችና የበሰበሱ ናቸው- ብሎ ተናግሮ ነበር። 391 ….በተለይ አዲሱ አፈንጋጮች የበሰበሱና ጠባቦች ነበሩ እያለ የትግራይ ህዝብ በተለየ ሁኔታ ተጠቃሚ ሆኗል የሚለውን የመለስን የፕሮፖጋንዳ ጨዋታ ከመጠን በላይ ያራግበው ነበር። (ገጽ 392) ። በአቶ መለስ እርዳታ ከጀኔራሎችም እነ ባጫ ደበሌ ሳይቀሩ የትግራይ ገበሬዎች
የበለጠ ተጠቃሚ ሆነዋል ሁሉ ነገር ትግራይ ትግራይ ብቻ መሆን የለበትም ብለው እስከመናገር መድረሳቸውና ሥርዓቱን በጠባብ ብሔርተኝነት መክሰሳቸው ታይቷል።

አቶ መለስ የፓርቲ አባሎቻቸው ድጋፍና ድምጽ በጎደላቸው ወቅትም ባለቤታቸውና ማሰማራታቸውን ገብሩ ጽፈዋል። “አዜብ ለመለስ ድጋፍ ለመሰብሰብ በቤተ መንግሥት ቅልጥ ያለ ግብዣ እያዘጋጀች ማዕከላዊ ኮሚቴ አባላትን ታምበሸብሽ ነበር” ገጽ 351 ብለዋል። ከአቶ ገብሩ አጻጻፍ የዘወትር አቶ
መለስ አቋማቸውን በፍጥነት በመገለባበጥ የሚታወቁ የልባቸውን ካደረጉ በኋላ ፈጥነው ይቅርታ ተሳስቻለሁ ብለው አ ም ታ ተ ው እ ን ደ ሚ ያ ል ፉ የተለያዩ አጋጣሚዎችን እየጠቀሱ ጽፈዋል። ከሁሉም የእግር እሳት ሆኖ የሚያቃጥላቸው ኢትዮጵያን ሉዓላዊነት ዋስትና ሊሰጥ በሚችል መልኩ ሊጠናቀቅ ይችል ነበር ያሉት የኢትዮ-ኤርትራ ጦርነት ባልፈለጉት መንገድ ድንገት መጨናገፉ ነው። እንደገብሩ ገለጻ ለዚህ ዋነኛ ተጠያቂው አቶ መለስ ናቸው እንዲህ ጽፈዋል፦መለሰ በዚህ ዓይነት የተወሳሰበና ተንኮል የተሞላበት አግባብ ብቻውን ያደረገውን የጦርነቱን ሂደት የማስቆም ውሳኔ ተገቢ እንዳልነበረና ይህን ለመወሰንና ለማወጅ የሚያስችል ሥልጣን እንዳልነበረው ኋላ ላይ ሂስ ሲቀርብለት “አዎን ስህተት ፈጽሜያለሁ ሆኖም ከጦር ግንባር ሳገኘው የነበረው መረጃ ጦርነቱን ለማስቀጠል ያስችላል የሚል ስላልነበረ ከዚህ ተነስቼ ጦርነቱን በ24 ሰዓት ውስጥ እንዲቆም አውጃለሁ። የሥራ ባልደረቦቼን ማማከር ነበረብኝ ይህን ባለማድረጌ ተሳስቻለሁ።” አብዛኛዎቹ የማዕከላዊ ኮሚቴ ወታደራዊ እዝ አባላትና የኢሕአዴግ ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባላት አዋጁን የሰማነው እንደተራው ዜጋ በመገናኛ ብዙኃን ስለነበር አዋጁ የተጣደፈው ምናልባት በግንባር የነበሩት አዛዦች ግምገማቸውን አስተላልፈው መቀጠል እንደማይችሉ ስለገለጹ ሊሆን ይችላል የሚል ግምት ነበረን። ነገር ግን የግንባር አዛዦቹ ግምገማ ለማዕከላዊ እዙና ለሥራ አስፈጻሚው አባላት የደረሰው መለስ ጦርነቱ እንዳበቃ ካወጀ ከቀናት በኋላ ነበር። ይህ በመሆኑ የግንባር አዛዦቹ ግምገማ እርሱ ከሚፈለገው ውጭ እንደማይሆን አስቀድሞ በደጋፊዎቹ ተነግሮታል የሚል ግምት አለኝ። ሳሞራና ተከታዮቹ ከነዚህ ህወሓት ውስጥ ቴክኒካል አሬንጅመቱን ተቀብለን እንፈርም ከሚሉ ወገኖች ጋር ጥብቅ ግንኙነት ነበራቸው። 314-315

በተቃዋሚዎች ምሽግ ላይ እልል በል!- አብ ዱፋዖም አልል!

በአጠቃላይ የመንግሥት ሥልጣን ከመቆጣጠራችን በፊት ስንጠቀምባቸው የነበሩትን ጠላትና ወዳጅ የሚለዩ ፅንሰ ሐሳቦች መንግሥት ካቋቋምን በኋላም አላስወገድናቸውም ነበር። 186 አብ ዱፋዖም አልል- በምሽጋቸው ላይ እልል በል! በ002 ምርጫ ወቅት ኢህአዴግ ያልተገበረው የአፈና ስልትና ያላካሄደው ከባ አልነበረም። ወቅቱ ነጻና ፍትሀዊ ምርጫ የተካሄደበት ሳሆን በተቃዋሚዎች ላይ ግልጽ ጦርነት የታወጀበት እንበር። ለነገሩ በዚህ የምርጫ ዋዜማ ህወሓት/ኢህ አዴግ አብአብ ዱፋዖም አልል- በምሽጋቸው ላይ እልል በል! የሚለውን የትጥቅ ትግል የድል ዘፈን በተደጋጋሚ ያስዘፍን ነበር። ይህ የዋዛ ቢመስልም መልዕክቱን በጥልቀት ለተመለከተው በተቃዋሚዎች ላይ እንደ ደርግ ጦርነት መታወጁ ግልጽ ነበር።463

ትግራይና ኤርትራ – አንቺው
ታመጪው አንቺው ታሮጪው

አቶ ገብሩ ስለ ህወሓትና ሻዕቢያ ግንኙነት አንድነትና ልዩነት ሲናገሩ የሚከተለውን ብለዋል ” እውነቱን ለመናገር ግን ግኙነታችን ሞቅ ሲል ልክ እንደ አንድ ድርጅት በጋራ የምንሠራበት ግንኙነቱ ሲቀዘቅዝ ደግሞ በዓይነ ቁራኛ የምንተያይበት ሁኔታ ነበር እንጂ ግንኙነታችን ስትራቴጂያዊ አይደለም የሚለው አቋማችን ግንኙነትቻን ላይ ስለሚኖረ ተጽ እኖ በግልጽ ተዘርዝሮ አልተቀመጠም ነበር። ስለዚህ ከሻ ዕቢያ ጋር አሉን ያልናቸው የፖለቲካ ልዩነቶቻም የይዘት ሳይሆን የስም ብቻ እንደነበሩ እነዚህ ያደረግናቸው የፖለቲካ ለውጦች ያሳያሉ…በመሆኑም ሁለቱም ድርጅቶች በተጨባጭ ከቃላት ያለፈ የር ዕዮት ዓለምም የስትራቴጂም ልዩነት አልነበራቸውም ማለት ይቻላል። (ገጽ 236)ስለዚህ በሁለቱ መካከል የዓላማም ሆነ የስትራቴጂም ልዩነት ከሌለ ወደ ግጭት የወሰዳቸው ወይም ህመማቸው ታዲያ ምንድነው የሚል ጥያቄ ያጭራል። አቶ ገብሩንና መሰሎቻቸውን ሁሌም የሚያበግናቸው ነገር ከበረሃ ጀምሮ የሻዕቢያ ባለሥልጣናት ለህወሓት ባለሥልጣናት የሚያሳዩት ንቀትና የሚፈጽሙት የትዕቢት ድርጊት ነው። እንደገብሩ መጽሐፍ ያኔ ሁለቱ ሻዕቢያና ህወሓት ወዳጅ መንግሥታት በነበሩ ጊዜ ኢሳያስ ምንም የፕሮቶኮል አግባብ ሳይጠብቁ መኪናቸውን አስነስተው መቀሌ ይገቡ ነበር። ከካርቱም አልበሽርን ከአዲስ አበባ አቶ መለስን ይዘው መቀሌ ላይ ስብሰባ ይቀምጡ ነበር። ሌላው ቢቀር ፕሮቶኮል አለመጠበቁን ያማርሩ የነበሩት የወቅቱ ፕሬዚዳንት ዶ/ር ነጋሶም ስለ ጉዳዩ ቅሬታቸውን መግለጻቸውን እንዲህ ሲሉ ጽፈዋል”

“የወቅቱ የኢትዮጵያ ፕሬዚዳንት ነጋሶ በሽርና ኢሳያስ አፈወርቂ ያለ እርሱ እውቅና በበርካታ አጋጣሚዎች ወደ ኢትዮጵያ እንደሚመጡና ….365 ሲያሰኘን እንደ መንግሥት ሲያሰኘን እንደታጋይ ሆነን የፈለግነውን እንግዳ ወደ ኢትዮጵያ ስናስገባና ስናስወጣስ ነጋሶ ከፕሮቶኮልና ከአሠራር አንጻር ላነሳው ጥያቄ ክብደት ልንሰጠው በተገባ ነበር። በሽርና ኢሳያስ አዲስ አበባ ሳይደርሱ በቀጥታ ወደ መቀሌ መጥተው በወቅቱ ርዕሰ ብሔር ካልነበረው ከመለስጋ ሶስቱን አገሮች በሚመለከቱ ጉዳዮች ላይ ብዙ ጊዜ ይነጋገሩ ነበር። 365ይህ የሚሆነው እንግዲህ አቶ ገብሩ ፕሬዚዳንት ሆነው በሚያስተዳድሯት የትግራይ ክልል ዋና ከተማ መቀሌ ውስጥ ነው። ይህም ሳይበቃ ለኤርትራ አዋሳኝ በሆነቸው የትግራይ ክልልና ድንበር ውስጥ በሚፈጸሙ አንዳንድ ቅሬታዎች የተቆጡት አቶ ኢሳያስ በአስመራ የኢትዮጵያ አምባሳደር ለነበሩት አቶ አውአሎም ዛሬ ሄጄ ገብሩን ሰድቤ እመጣለሁ ብለው እየነዱ እንደሚመጡ ገብሩ ጽፈዋል።
ዋነኛው ችግርና ለግጭት ያበቃቸው ምክንያት ግን የኢኮኖሚ ግኙነት መሆኑን አቶ ገብሩ በመጽሐፋቸው ለማሳየት ሞክረዋል። ይህም ቢሆን ኤርትራን አምራች ኢትዮጵያን ሸማች ከማድረግ ኤርትራን መሪ ኢትዮጵያን ተከታይ የማድረግ አዝማሚያ መታየቱ ዋነኛው ሰበብ ይመስላል። መጽሐፉ “ ሻዕቢያዎች ኢትዮጵያን ለመቆጣጠር ስለነበራችው ህልምና ነጻነታቸውን ባወጁ ሁለተኛው ወር ላይ ሐምሌ 1983 ከፍተኛ የኢኮኖሚ ኮንፈረንስ ማዘጋጀታቸውን፣ በኮንፈረንሱም የኢትዮጵያን አየር መንገድ እንደገና አዋቅሮ ከኤርትራውያን ጋር የጋራ አክስዮን ኩባንያ እንዲፈጠር፣ ትግራይ ውስጥ የሚሠራውን የመንገድ ፕሮጀክት ሁሉ ኤርትራውያን እንዲገነቡት፣ ቀይ ባህር የንግድ ድርጅት በሚል አንድ የንግድ ኩባንያ እንዲቋቋም ማንኛውም ኤርትራዊ 500 ብር አውጥቶ አክስዮን እንዲገዛ የመሳሰሉት ውጥኖች መኖራቸው በመጽሀፉ ተመልክቷል፡፡ አስመራና መቀሌ ላይ ብዙ ምክክሮች ቢደረጉም ጨርሶ ሊስማሙ የሚችሉበት ሁኔታ ግን አልነበረም።ከዚያም አልፎ ወደ በጥቃቅን ጉዳዮች ሁሉ ወደ መጨቃጨቅና የንግድ ልውውጥና የገንዘብ ዝውውርን እስከ መገደብ ተደረሰ። ሁኔታው ከባለሥልጣናቱ እጅ ወጥቶ ወደ ህዝብና ሚዲያ ጆሮ መድረስ ጀመረ። ኤርትራን የሚከሱት አቶ ገብሩ አንዱን ምናልባትም የግንኙነት
መበጠሻ የሆነውን የመጨረሻ አጋጣሚ እንደሚከተለው ገልጸውታል፦

በሻዕቢያ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ከፍተኛ የፀረ- ትግራይ ቅስቀሳ ይደረግ ነበር።“በአንድ ወቅት ከትግራይ ወደ ኤርትራ የሚገባውን ማንኛውንም ሸቀጥ በመከልከል ጉሮሮአችንን ለማነቅ እየተንቀሳቀሱ ነው ነው የሚል የፕሮፖጋንዳ ዘመቻ ይደመጥ ነበር። ይህን የሰሙ ኢትዮጵያውያን ኤርትራውያንና የተወሰኑ የሻ ዕቢያ አባላትት እጅግ ተደናግጠው ምን እየተደረገ እንው? ይህ የፕሮፖጋንዳ ዘመቻስ ወዴት እያመራ ነው?” የሚል ስጋት አድሮባቸው ነበር። ኢሳያስ የመጨረሻውን ስብሰባ ከኛ ጋር ሲያደርግም “የዚህ ዓይነት ዘመቻ እየተኪያሄደ ያለው ለምንድነው? ብለን ስንጠይቀው ለጥያቄያችን ያህን ያህል ክብደት
ሳይሰጠው “የምታነሱት ነገር በሚዲያ ሲተላለፍ ባልሰማም ሰዎች ሲንጫጩ ሰምቼ እስቲ በቴሌቪዥን የተላለፈውን አሳዩኝ ብዬ ምጽዋ ላይ ተመልክቼው ነበር። የተላለፈው መልዕክት ትንሽ የተጋነነ ቢሆንም መሠረታዊ ስህተት ግን አላየሁበት። አሁንም ትግራይ ጉሮሮአችንን ለማነቅ እየተንቀሳቀች ነው።
ብሎ አረፈው። 256ይህን ካለ በኋላም ኢትዮጵያ ኤርትራ ያቀረበቻቸውን የኢኮኖሚና ማህበራዊ ጥያቄዎች ብትመልስ እንድሚሻላት ደጋግሞ አሳሰበን። በኛ በኩል ደግሞ እየቀረበ ያለው ጥያቄ አግባብነት እንደሌለው ደጋግመን መለስንለት። “መልሳችሁ ይህ ከሆነ ከ እንግዲህ በሁለት አገሮች መካከል ግንኙነት ልሊኖር አይችልም አለ። እንዲያውም ድንበራችንን የሚያካልል ኮሚቴ(በአስቸኳይ) ይቋቋም የሚላ አሳብ አቀረበ። 256ወደ አዲስ አበባ ከተመለስን በኋላ አስመራ ላይ የሆነውም ሁሉ ለመግለጽ አስችኳይ የህወሓት ሥራ አስፈጻሚ ስብሰባ እንዲጠራልን መለስን ጠየቅነው። ሻዕቢያ ወረራ ያካሂዳል ብለን እናምናለን አናምን ተብሎ በተሰጠ የፖሊት ቢሮው ድምጽ መለስ ዜናዊ ስዩም መስፍን ስዬ አብርሃ ስብሐት ነጋ ክንፈ ገ/መድህን ሲሆኑ ወረራ ያካሂዳል ብለን እናምናለን ያሉት ዓባይ ተወልደ ወልደ ማርያም፣ ዓለምሰገድ ገ/አምላክ ዓባይ ፀሐዬ እና ገብሩ አስራት ነበሩ። (ገጽ 258) በፀረ ሻዕቢያ አቋማቸው ይታወቃሉ የተባሉት አቶ ስዬ አብርሃ እስከዚያ ድረስ ታውረው ነበር ማለት ይሆን? እስከ ህወሓት አምስተኛው ጉባኤ ድረስ አልነቁም ነበር።

ከዚያ በኋላ የአቶ ገብሩ መጽሀፍ እንደሚያትተው አይቀሬው ጦርነት ተካሄደ። በጦርነቱ ዙሪያ በተያዘው አቅዋምና እሱን ተከትሎ በተነሳ ክፍፍል አቶ መለስ ተቀናቃኞቻቸውን በሙሉ እንዴት አድርገው ከፓርቲው እንዳባረሩ መጽሀፉ ይተረካል። መለስ የኢህአዴግ ጽ/ቤት እንዲታሸግና እንዲፈተሽ ማድረጋቸውን ለዚህም ደህነቱ አቶ ክንፈ ታዘው መፈጸማቸውን ያትታል። ከዚያ በኋላማ በቃ ከአቶ መለስ በስተቀር ሌላው የአመራር አባል ከራስ ጠጉሩ እስከ እግር ጥፍሩ እየተፈተሸ ወደ ስብሰባ አዳራሾች መግባት ጀመረ ብለዋል ከአፈንጋጮች አንዱ የተባሉት አቶ ገብሩ አስራት፡፡ አቶ መለስ በብቸኝነት ወጡ!እሱ በህይወት ኖሮ ይህን መጽሀፍ ባሳተምኩ ኖሮ ደስ ይለኝ ነበር ያሉት አቶ ገብሩ ይህን መጽሐፍ ለማሳተፍ ያሰብኩት ከመለስ ዜናዊ እልፈት በፊት ቢሆንም በተለያዩ ምክንያቶች አልተሳካልኝም ብለዋል። እሱ በሕይወት ኖሮ መልስ ቢሰጥበት ደስ ባለኝ” በማለት ይህ ባለመሆኑ ቅሬታ ንደሚሰማቸው
ገልጸዋል። አቶ መለስን በህይወት ያሉትንም ሰዎች የሚተቹት በቂም በቀል ሳይሆን ሥርዓቱን ለመተችት እንደሆነም ጽፈዋል። መልካም ንባብ! (ዘኢትዮጵያ)

ይድረስ አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ: ሕገ-መንገስቱ ተጣሰ፣ ሻለቃ መላኩ ተፈራ ታገተ

$
0
0

ለክቡር አቶ ኃይለማርያም ደሳለኝ
የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚኒስትር

ጉዳዩ፡- በኢፌዲሪ ሕገ-መንግሥት አንቀጽ 37(1) መሠረት ፍትሕ ለማግኘት ለሁለተኛ ጊዜ የቀረበ አቤቱታ፤

1. በኢፌዲሪ ሕገ-መንግሥት አንቀጽ 51(1) ሕገ-መንግሥቱን መጠበቅና መከላከል የፌዴራል መንግሥት ሥልጣንና ተግባር በመሆኑ፤

2. በኢፌዲሪ ሕገ-መንግሥት አንቀጽ 74(13) ሕገ-መንግሥቱን ማክበርና ማስከበር የጠቅላይ ሚኒስትሩ ሥልጣንና ተግባር በመሆኑ፤ አቤቱታዬን እነሆ ለሁለተኛ ጊዜ ለክቡርነትዎ ለማቅረብ ተገድጃለሁ፡-

ጅቡቲ በስደተኞች ሰፈር በምኖርበት ቤት ውስጥ ታሕሣሥ 26 ቀን 1985 ዓ.ም. ከምሽቱ 3 ሰዓት በቅጥር ነፍሰ ገዳዮች በተፈጸመብኝ የመግደል ሙከራ ከፍተኛ ጉዳት ደርሶብኝ፣ በጅቡቲ ሆስፒታል ለ1 ዓመት ከ3 ወራት በሕክምና ስረዳ ቆይቼ በእግዚአብሔር ቸርነት ከሞት ልተርፍ ችያለሁ፡፡ በወቅቱ በጭካኔ ከተደበደብኩባቸው 9 ጥይቶች መካከል አንዱ ጥይት አሁንም በሰውነቴ ውስጥ ስለሚገኝ ከሳምባዬ ጋር በሚያደርግው ንክኪ በየጊዜው ለከባድ የሳል ሕመም የሚዳርገኝ መሆኑን በሐኪም ተረጋግጦ ተነግሮኛል፡፡ ለዚህ የወንጀል ድርጊት ተጠያቂ የሆኑት ሰዎች ግን ዛሬም የመንግሥት ሥልጣናቸውን መከታ አድርገው ከእሥር እንዳልፈታ የተለመደ የበቀል እርምጃ በመውሰድ ላይ ናቸው፡፡ አልፎ ተርፎም ከማረሚያ ቤት ብወጣም ሕይወቴ በእነሱ እጅ እንደሆነና የሚፈልጉትን ማድረግ እንደሚችሉ ዛቻዎቻቸው እየደረሰኝ ነው፡፡ ይሁን እንጂ ደምን በደም ቢያጥቡት ተመልሶ ደም ነው፡፡
pen
የሆነው ሆነ ይህንን ማመልከቻ ልጽፍልዎ የተነሳሁበት ዋና ምክንያት፣ በኢፌዲሪ ሕገ-መንግሥት አንቀጽ 25 እና በኢፌዲሪ የወንጀል ሕግ አንቀጽ 4 ‹‹ሁሉም ሰዎች በሕግ ፊት እኩል ናቸው›› የሚለውን ድንጋጌ በሚቃረን መልኩ በዜግነቱ በዕኩልነት የመታየትና የመዳኘት ሕገ-መንግሥታዊ መብቴ በመጣሱ የተነሳ ከፍተኛ ጉዳት ስለደረሰብኝ፤ ፍትሐዊ ውሳኔ ይሰጡኛል በሚል እምነት ሰኔ 7 ቀን 2006 ዓ.ም አቤቱታዬን በጽሑፍ ለክቡርነትዎ ማቅረቤን ያስታውሱታል ብዬ አምናለሁ፡፡ እንደሚታወቀው በኢፌዲሪ የወንጀል ሕግ አንቀጽ 202(1) ማንኛውም ተቀጪ ፍርዱ የዕድሜ ልክ እስራት ከሆነና ታሳሪው ሃያ ዓመት ከታሰረ፣ ፍርድ ቤቱ ጥፋተኛው በአመክሮ እንዲፈታ እንደሚወስን ተደንግጓል፡፡ በዚህ መሰረት እኔም በተከሰስኩበት ጉዳይ እጄ ከተያዘበት ከ22/8/1986 ዓ.ም. አንስቶ የተፈረደብኝን የእድሜ ልክ እሥራት (20 ዓመት) በ22/8/2006 ዓ.ም. ጨርሻለሁ፡፡ ሆኖም ከ23/8/2006 ዓ.ም ጀምሮ በማላውቀው ጉዳይ ሕገ-መንግስታዊ መታግቼ አሁንም በአዲስ አበባ ማረሚያ ቤት /ቃሊቲ/ ዞን አራት ውስጥ በእሥር ላይ እገኛለሁ፡፡ ማረሚያ ቤቱ የአመክሮ መብትን ለማክብር ታራሚው በእስር ቤት ቆይታው ያለውን ባሕሪ መገምገም እንዳለበት አውቃለሁ፤ በዚህ መሰረትም እኔ 20 ዓመት በእሥር በቆየሁበት ጊዜ የነበረኝ ጠባይ ተገምግሞ ያገኘሁት ውጤት እጅግ የሚያስመሰግነውን ዘጠና አምስት ከመቶ (95%) ነው፡፡ ይህም በማረሚያ ቤቱ ኃላፊ በአቶ አብርሃም ወልደአረጋይ ፊርማ ተረጋግጦ፣ ለፍቺ ከሌሎች ታራሚዎች ሠነዶች ጋር በ9/8/2006 ዓ.ም. ለፍርድ ቤት ተልኮ የነበረ ቢሆንም፤ በ17/8/2006 ዓ.ም. ለፍርድ ቤት ከተላኩት ሠነዶች መካከል የእኔን ብቻ ነጥለው መለሰው በማስመጣ ራሳቸው አቶ አብርሃም ወልደአጋይ በእጃቸው እንደያዙት በማረሚያ ቤቱና በፍርድ ቤቱ ሠራተኞች ተረጋግጦ ተነግሮኛል፡፡ ይህን የሚያስረዳ የፍርድ ቤቱ ማረጋገጫ ሠነድም ከዚህ ጋር ተያይዟል፡፡ እኔም ሆንኩ ቤተሰቤ፣ አቶ አብርሃም ወልደአረጋይን ለማነጋገር ያደረግነው ጥረት ሊያነጋግሩን ፈቃደኛ ባለመሆናቸው ሊሳካልን አልቻለም፡፡

በኢፌዲሪ ሕገ-መንግሥት አንቀጽ 19(3) በወንጀል ተጠርጥረው የተያዙ ሰዎች በ48 ሰዓታት ውስጥ ፍርድ ቤት የመቅረብ መብት እንዳላቸው የተደነገገ ቢሆንም፤ እኔ ግን የተፈረደብኝን ቅጣት ጨርሼ ያለአንዳች ምክንያት ሕገ-መንግሥቱን በመጣስ እስከ ዛሬ (ነሐሴ 17 ቀን 2006ዓ.ም) ድረስ 115 ቀናት ወይም 2760 ሰዓታት ታግቼ እገኛለሁ፡፡

ክብሩ ጠቅላይ ሚኒስትር

በፌዴራል ማረሚያ ቤቶች ኮሚሽን ማቋቋሚያ አዋጅ ቁጥር 365/1999 አንቀጽ 39(1) መሠረት በወጣው የፌዴራል ታራሚዎች አያያዝ የሚኒስቴሮች ምክር ቤት ደንብ ቁጥር 138/1999 አንቀጽ 44(1) ስለማረሚያ ቤቱ ግዴታ እንደሚከተለው ተደንግጓል፡፡
‹‹ማንኛውም ታራሚ የእሥራት ጊዜውን ሲጨርስ፣ ይቅርታ ወይም ምሕረት ሲያገኝ ወይም ፍርድ ቤት በአመክሮ እንዲፈታ ትእዛዝ ሲሰጥ ማረሚያ ቤቱ ታራሚውን ወዲያው የመፍታት ግዴታ አለበት››፡፡
ነገር ግን እኔን ለመጉዳት ሲባል ብቻ ይህ ደንብ ሊጣስ መቻሉን ክብሩነቶ እንዲያውቁት ነው፡፡

እንዲሁም በኢፌዲሪ ሕገ-መንግሥት አንቀጽ 9(1) የሕገ-መንግሥቱ የበላይነት እንደሚከተለው ታውጇል፡-
‹‹ሕገ-መንግሥቱ የበላይ ሕግ ነው፡፡ ማንኛውም ሕግ፣ ልማዳዊ አሠራር፣ እንዲሁም የመንግሥት አካል ወይም ባለሥልጣን ውሳኔ ከዚህ ሕገ-መንግሥት ጋር የሚቃረን ከሆነ ተፈጻሚነት አይኖረውም›› ተብሎ የተደነገገ ቢሆንም አሁንም እኔን ለመጉዳት ሲባል ብቻ ይህ የሀገሪቱ ሕገ-መንግሥት ተጥሷል፡፡
ስለዚህም እስከ ዛሬ ድረስ ከነቤተሰቤ የደረሰብኝን የረዥም ጊዜ ተደራራቢ ችግር በጥሞና ተረድተውልኝ በሕገ-መንግሥቱ የበላይነት ከእስር እንድፈታ ክቡርነትዎ ለማረሚያ ቤቱ ኃላፊ ለአቶ አብርሃም ወልደአረጋይ ትእዛዝ እንዲሰጡልኝ በማክበር አመለክታለሁ፡፡
ሻለቃ መላኩ ተፈራ ይመር

እኛ ኢትዮጵያውያን ለውጥ እንፈልጋለን ስንል ሌላ ትርጉም እስካልተሰጠው ድረስ ለውጥ እንፈልጋለን ማለታችን ነው

$
0
0

ስብሃት አማረ

Justiceእንደሚታወቀው ላለፉት 23 አመታት በኢትዮጵያ ሕዝብ ጫንቃ ላይ የተቀምጠውን ዘራፊውን እና ጨቋኙን የወያኔ ጁንታ በጀመርነውና በተያያዝነው አዲስ አመት ለመቅበር የአንድነት እና የለውጥ ሃይሎች ልዩነቶቻችንን በማቻቻል በጋራ ልንታገል የሚገባና ለህዝባችንና ለሃገራችን ስር ነቀል ለውጥ ልናመጣ የሚያስችለንን ምዕራፍ  የምንጀምርበት አመት መሆን አለበት። ባሳለፍናቸው በርካታ  የትግል አመታት ውስጥ የተቃዋሚዎች እርስ በእርስ መፈራረጅና መወነጃጀል  የወያኔን እድሜ ከማራዘም ውጪ ለኢትዮጵያ ሕዝብ ያተረፈው  አንዳችም ነገር የለም። የአንድነት የተቃዋሚ ሃይሎች ጥንካሬ እንዲጎለብት በየድርጅቱ ውስጥ ያሉትን እንከኖች በማጥራት በጋራ እና በተቻቻለ የሃሳብ መግባባት ተቻችሎ እና ተግባብቶ ሁለገብ የትግል ስትራቴጂን ከግብ ለማድረስ ጠንክሮ መስራት ይጠበቅብናል።

የኢትዮጵያ ሕዝብ ለውጥ ይፈልጋል። ኢትዮጵያውያን ለውጥ እንፈልጋለን ስንል እውነተኛና ዴሞክራስያዊ የሆነ ለውጥ እንፈልጋለን ማለታችን ነው ። ለለውጥ፣ ለፍትህና ለእኩልነት ነገ የምንጠብቀውንና የምንናፍቀውን የማይቀረውን ዴሞክራሲያዊ የመንግስት ለውጥ እስከምናገኝ ድረስ እንደትናንቱ ዛሬም አሁንም ድምጻችን እንዲሰማ እንጮሃለን።

በሃገሪቱ ያለውን ሁኔታ በትክክለኛው መንገድ የማያስቀምጡ የወያኔ ሚዲያዎች እርስ በእርሳቸው የሚጋጩ ዘገባዎችን በመስራት እና እውነትን ለመሸፋፈን በመትጋት የሕዝቦችን የማወቅ መብት ያለርሕራሄ እየተጋፉት/እየገፈፉት ይገኛል። ይህ በወያኔ የፕሮፓጋንዳ አካላት የሚፈጸም ማጭበርበር እና ማደናገር የገዢውን ፓርቲ ውስጣዊ ዝርክርክነት በይፋ ያሳብቃል። የሌለውን እንዳለ፤ ያልተሰራውን እንደተሰራ፤ ሕዝቡ የማያገኘውን አገልግሎት እንደሚያገኝ፤ ወዘተ በማድረግ በተጋነነ ሁኔታ ባልሆነ ስሌት በማባዛት በመቶኛ በማስላት በመደመር በማባዛት የሌለ ምስልን በመፍጠር ሕዝቡንና እርዳታ ሰጪ መንግስታትን ለማደናገር  ይሞክራሉ።

ፍትሕ  አጣን፣ ፍትሕ ዘገየብን፣ ፍትሕ ተነፈግን የሚሉ በርካታ ዜጎች ባሉበት አገር ውስጥ የፍትሕ ሥርዓቱ ተደራሽነት ወደር እንደሌለው የሚደሰኩሩ  የመንግስት ሪፖርቶችና መግለጫዎች የሚያስገርሙ ናቸው፡፡ ሕዝቡ በየፍርድ ቤቱ በተጓደለ ወይም በተነፈገ ፍትሕ ምክንያት ከላይ ታች ሲባዝን/ሲንከራተት እየታየ የማይመስልና የሌለ ነገር  ይነገራል፡፡ ከሰሞኑእንኳን ጋዜጠኞችና ጦማሪያኑ መንግስት ያወጣውን ህግ እንዲያከብር ስለጠየቁና በአደባባይ ስለጻፉ ግፍ እየተፈጸመባቸው እንደሚገኝ የአለም ህዝብ እንዲሁም የሰብዓዊ መብት ተከራካሪ ድርጅቶች ያወገዙት የወያኔ ተግባር ነው። በየእስር ቤቱ የሚማቅቁትንና የግፍ ግፍ እየተፈጸመባቸው ያሉት በነርዕዮት፣ ውብሸት፣ አንዷለም፣ እስክንድርና በሌሎችም ላይ እየተደረገ ያለው ስቃይና እንግልት ሳያንስ ሰሞኑን ደግሞ የሚወዱትን ህዝብ፣ የሚወዱትን ሃገርና የሚወዱትን ሞያቸውን በመተው የተሰደዱትን ጋዜጠኞች ማስታወስና እየከፈሉ ያሉትን መስዋእትነት መዘከር ያስፈልጋል። እኚህ የተሰደዱትና የታሰሩት ጋዜጠኞችና ጦማሪያን ያሸበሩት ሀገርና ህዝብ የለም፥ መንግስት ያወጣውን ህግ እንዲያከብር ለህግም ተገዢ እንዲሆን ጠየቁ እንጂ ።

ሌላው በየአካባቢው ‘ቀና ብለህ ባለስልጣን ተናገርክ፣ አግባብነት የሌለው ጥያቄ ጠየቅህ፣ ባለስልጣን ተዳፈርክ፣ ከሁለት በላይ ተሰብስበህ አየንህ’ ወዘተ እየተባለ የሚገረፈው፣ እንደ እንስሳ እየተገደለ የሚጣለው ኢትዮጵያዊ የሰራው ወንጀል የለም። በፍጹም አሸባሪም አይደለም! በየቦታው ቦንብ እየቀበረ ወይንም እያስቀመጠ አፈንድቶ ንጹሃንን ገድሎ ሲያበቃ ‘ሊያፈነዱ ሲሉ ተደረሰባቸው’፣ ወይንም ‘ፈንድቶባቸው ራሳቸውን ገደሉ’ ብሎ ውዥንብር የሚነዛው አሸባሪው ህወሃት እንጂ ንጹሃኑ ኢትዮጵያዊ እንደአይደለ የታወቀ ነው።

ተደጋግሞ ከተለያዩ የህግ ባለሙያዎች እንደተገለጸው አለምዓቀፍ ህግን በተጻረረ መልኩ ኦኬሎ አኳይንና አንዳርጋቸው ጽጌን ከመንገድ ያውም ከሰው አገር በጉቦ አስጠልፈውና አፍነው በመውሰድ ያው የተለመደ  ግፋቸውን እየፈጸሙ ይገኛሉ፣ ይህ የሚያሳየው ወያኔ እጁ ምን ያህል ረጅም እንደሆነ ነው። እነዚህ ሁለት የፍትህና የእኩልነት ታጋዮች ኦኬሎ አኳይንና አንዳርጋቸው ጽጌ ራሳቸውን ዝቅ አድርገው እንደ ሌሎች የተቃዋሚ መሪዎች የበኩላቸውን ለማበርከት ደፋ ቀና ሲሉ በወያኔ መረብ ውስጥ ቢገቡም ለፍትህና ለእኩልነት እንዲሁም ለሃገር ነጻነት የከፈሉት አስተዋጽኦ መቼም የማይረሳ ታላቅ መስዋእትነት ያበረከቱ የኢትዮጵያ የቁርጥ ቀን ልጆች ናቸው።

በአጠቃላይ ሲታይ ኢትዮጵያ ያለችበት ሁኔታ አሳሳቢና አስጊ  የመሆኑን ያህል የወያኔ አባልና ደጋፊ  ‘ጤነኛ’ ለሃገር አንድነትና ለፍትህ የሚከራከረው ተቃዋሚው ወገን ደግሞ ‘አሸባሪ’  የሚል አጸያፊ ተቀጥላ በማበጀት ንጹሃኑን በየእስር ቤቱ በማጎር ህዝባዊውን ትግል ለማኮላሸት በመፍጨርጨ ላይ ይገኛል፡፡

ትግልን በጋራና በውህደት ማቀናጀት ወቅቱ የሚጠይቀው ሁኔታ እንደሆነ እየታዩ  ያሉት አንዳንድ ምልክቶች አሉ፣ በመሆኑም ኢትዮጵያንና ሕዝቧን ካሉበት አዘቅት በማውጣት ሕዝቡ የስልጣን ባለቤት የሚሆንበትን ሁኔታ ለማመቻቸት የጋራ ትግልና መስዋዕትነት የግድ የሚል ደረጃ ላይ በመድረሱ፤ የወያኔን ቡድን በሁለገብ ትግል በመፋለም በኢትዮጵያ አንድነት የሚያምኑ ድርጅቶች ተጣምሮና አንድ ሆኖ መታገል እንዳለባቸው ከሰሞኑ የተወሰዱት የ3 ድርጅቶች የውህደት ንግግርና ስምምነት ያሳያል።

ወቅቱ ለጠየቀው የሀገር አድን ጥሪ ምላሽ በመስጠት የኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባር የአርበኝነት ትግል ችቦውን በመለኮስ እንደ ሻማ በመቅለጥ ብርሃን እየሰጠ ያለ ግንባር እንደመሆኑ መጠን የተለኮሰውም የትግል ችቦ ሳይጠፋ የታለመለትንና ለታቀደለን አላማ እስከግብ ድረስ እንዲዘልቅ የወያኔን አገዛዝ እድሜ ለማሳጠር ትግሉን በማጠናከር በአሁኑ ሰዓት ግንባሩ ከግንቦት 7 የፍትሕ የነፃነትና የዴሞክራሲ ንቅናቄ እንዲሁም ከአማራ ዴሞክራሲያዊ ኃይሎች ንቅናቄ ጋር ውህደት ለማድረግ መስማማታቸው የሚያስመሰግንና ለሌሎችም የአንድነት ሃይሎች ተባብሮ የመስራትን ነገር ማሳያ በመሆን አስፈላጊ የሆነ ጥርጊያ መንገድ ይከፍታል/ከፍቷል። ውህደቱ ተጠናቆ የድሉን ፍሬ ተቋዳሽ የምንሆነበት ጊዜ ሩቅ እንደማይሆን አምናለሁ።

ስለዚህ ኢትዮጵያውያን የአንድነት ሃይሎች በመተባበር፣ በመጣመርና በመዋሃድ ሃይልን፣ እውቀትን፣ ህብረትን እንዲሁም ገንዘብን በማቀናጀት የወያኔን አገዛዝ ከኢትዮጵያ ምድር ወደ ከርሰ መቃብር ለአንዴና ለመጨረሻ አሸቀንጥሮ ወርውሮ ሃገርንና ህዝብን ለነጻነት ለማብቃት በጋራ መታገል ግዴታችን መሆኑን አውቀን በአንድነት ስርዓቱን ማስወገድ ማንኛውም ሃገሬንና ህዝቤን እወዳለሁ የሚል ዜጋ ሊነሳለት እና ሊተገብረው የሚገባ መሆኑን በመግለጽ የበኩሌን ሃሳብ ለማቅረብ እወዳለሁ::

አንድነት ኃይል ነው !!

ድል ለሰፊው ለኢትዮጵያ ሕዝብ !!

 

 

 

ቴዲ አፍሮ ከ9 ዓመት በፊት ሆላንድ መድረክ ላይ የተጫወተው ዘፈን እንደአዲስ መለቀቁን “ሕጋዊነትን ያልተከተለ ስርጭት”አለው

$
0
0

(ዘ-ሐበሻ) ዛሬ በሶሻል ሚዲያዎች ከፍተኛ አድማጭን ያገኘውን “ቀስተዳመና” የተሰኘውን ነጠላ ዜማ በማሰመልከት ቴዲ አፍሮ በፌስቡክ ከገጹ በሰጠው ቃል “ሕጋዊነትን ያልተከተለ ስርጭት” ሲል አወገዘው።
Teddy Afro Teddy Afro rocks ESFNA Closing Night 2013 (video)
አርቲስቱ በፌስቡክ ገጹ እንዳለው “ቀደም ሲል (ሰባ ደረጃ) በሚል ርዕስ አርቲስት ቴዎድሮስ ካሳሁን በኦፊሻል ድረ ገጱ ላይ አዲስ ሙዚቃ መልቀቁ ይታወቃል። ነገር ግን የዚህን ስራ መዉጣት ተከትሎ በቅርብ ጊዜ ዉስጥ ከአርቲስቱ እዉቅና ዉጪ በሶሻል ሚዲያዉ ላይ የተሰራጨ ሕጋዊነት የሌለውና ከዘጠኝ አመት በፊት አርቲስቱ በሆላንድ አገር መድረክ ላይ የተጫወተዉን ጥራቱን ወይም ደረጃዉን ያልጠበቀ ሙዚቃ ባልታወቁ ወገኖች እንዲሰራጭ ተደርጓል። ይህ እንዲሆን ያደረጉት ወገኞች ምክንያትም ሆነ ምንጭ ለጊዜዉ ባይታወቅም፡ ጉዳዩ ከአርቲስቱ የኮፒራይት መብት አንጻር ሲታይ ሕጋዊነትን ያልተከተለ በመሆኑ እዉቅና የሌለዉ ስርጭት መሆኑን ለአርቲስቱ አድናቂዎችና ወዳጆች በሙሉ ለመግለጽ እንወዳለን።”

የበረከት ጤና –ከኢየሩሳሌም አረአያ

$
0
0

bereket
አቶ በረከት ስሞኦን በሳኡዲ አረቢያ የልብ ቀዶ ህክምና እንዳደረጉ ታማኝ ምንጮች አረጋገጡ። በደቡብ አፍሪካ ከአመታት በፊት (ፔስ ሜከር) የተባለ የልብ ምትን የሚያስተካከል በረከት እንደተገጠመላቸው ያስታወሱት ምንጮቹ ይህ በመበላሸቱ ምክንያት የበረከት ህይወት አጣብቂኝ ውስጥ ወድቆ እንደነበረና በቅርቡ አልሙዲ ሳኡዲ ወስደው ይህ እንዲስተካከል በማደረጋቸው የበረከት ጤና ሊመለስ መቻሉን ምንጮቹ አስረድተዋል። በረከት ከጤናቸው ባሻገር በፖለቲካው መድረክ በነስብሃትና ደብረፂዮን በደረሰባቸው መገፋት እንደሚበሳጩ ምንጮቹ አመልክተዋል። በረከት ስሞኦን ለባለሃብቶች በቢሊዮን የሚገመት ብድር በመፍቀድ በከፍተኛ ሙስና ከተነከሩ ባለስልጣናት አንዱ መሆናቸውን የጠቆሙት ምንጮቹ ለአልሙዲና ለሳሙኤል የፈቀዷቸው ብድሮች በቂ ማስረጃ ናቸው ብለዋል። በረከትን ውጭ እየወሰዱ የሚያሳክሙት ደግሞ አልሙዲ ናቸው። በረከት ባለፈው ሳምንት በተካሄደው የፓርቲው ጉባኤ ተካፍለዋል።


Health: የሰውነት መቆጣት (አለርጂ)

$
0
0


አንዳንዴ ሰውነታችን አደገኛ ላልሆኑ ንጥረ ነገሮች በመቆጣት(በአለመቀበል) መልስ ይሰጣል። እነዚህ የመቆጣት መልሶች የሚቆረቁር አይን፣ ንፍጥ የሚወርድበት አፍንጫ፣ የሚከረክር ጉሮሮ፣ የቆዳ ሽፍታ፣ ማሳከክ፣ ማበጥ እና ውሃ መቋጠርን ሊያጠቃልል ይችላል። እነዚህ የሰውነት መቆጣቶች ሊያነሳሱ ከሚችሉት ንጥረ ነገሮች ምግብ፣ የጽዳት ኬሚካል፣ አየር ላይ የሚገኝ የአበቦች ፈሳሽ (ፖለን)፣ አቯራ እና እንስሶች ይገኙበታል።

ብዙ ሰዎች በሳር፣ የቢርችን ተክል እና ሌሎች ዛፎች ፈሳሾች ምክንያት የሰውነት መቆጣት ያጋጥማቸዋል። ከእነዚህ አትክልቶች የሚወጣው ፈሳሽ በፀደይ እና በበጋ ወቅቶች በብዛት ይታያል። በተለያዩ ጊዜአት የሚበቅሉ የተለያዩ የአበባ አትክልቶች እንደዚሁም ንፋስ እና የአየር ሁኔታ ለፈሻሾቹ መስፋፋት ወሳኝ ናቸው። ስለዚህም ስለ ፈሳሾቹ ማሰጠንቀቂያ ለማወቅ በአካባቢያችሁ የሚታተሙ ጋዜጦችን ማንበብ ጥሩ ሃሳብ ሊሆን ይችላል።

ከኖርዌይ ህዝብ 40 በመቶ የሚሆነው የሰውነት መቆጣት (አለርጂ) አለበት። እነዚህን የሰውነት መቆጣት ወይም አለርጂ ለመቆጣጠር የተዘጋጁ መድሃኒቶች አሉ። አንዳንድ መድሃኒቶችም የሀኪም ትዕዛዝ አያስፈልጋቸውም። ትክክለኛውን መድሃኒት ለመግዛት በአንደኛ የመድሃኒት መደብር በመሄድ እርዳታ ለማግኘት ይቻላል። ሌሎች መድሃኒቶች ግን የሀኪም ትዕዛዝ ያስፈልጋቸዋል። ስለ እነዚህ ሁለት መድሃኒቶች ተመለከተ መረጃ ለማግኘት ወደ ዶክተር መሄድ ጥሩ ነው። አንዳንድ መድሃኒቶች ለምሳሌ ክኒኖች ለሰውነት መቆጣት (አለርጂን) ይቀንሳሉ። ሌሎች ለምሳሌ ወደ አፍንጫ የሚረጩ ወይም የአይን ጠብታዎች ምልክቶቹን ይቀንሳሉ።

ወደ አዲስ ቦታ ሲጓዙ ቀደም ሲል አጋጥሞአችሁ የማያውቅ የሰውነት መቆጣት (አለርጂ) ሊያጋጥሙአችሁ ይችላሉ። እነዚህም በአካባቢ የሚገኙ ያልለመዳችሁት ነገሮች ወይም አዲስ ምግብ በማግኘታችሁ የሚከተሉ ሊሆኑ ይችላሉ።

የቂርቆስ ክፍለ ከተማ ሹሞች በመንግሥት ላይ ከ5.2 ሚሊዮን ብር በላይ ጉዳት በማድረስ ተጠርጥረው ታሰሩ

$
0
0

- ዋስትና ተከልክለው ወደ ማረሚያ ቤት ወርደዋል

የመንግሥትን ሥራ በማያመች አኳኋን በመምራት፣ በመንግሥት ላይ ከ5.2 ሚሊዮን ብር በላይ ጉዳት በማድረስ የሙስና ወንጀል የተጠረጠሩ የቂርቆስ ክፍለ ከተማ 11 ሹሞችና ሦስት ነጋዴዎች፣ ክስ ተመሥርቶባቸውና ዋስትና ሳይፈቀድላቸው ማረሚያ ቤት ወረዱ፡፡

የመንግሥትን ሥራ በማያመች አኳኋን በመመራት የሙስና ወንጀል ክስ መስከረም 5 ቀን 2006 ዓ.ም. በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ተረኛ ችሎት የተመሠረተባቸው ሹሞች የክፍለ ከተማው የንግድና ኢንዱስትሪ ልማት ጽሕፈት ቤት የገበያ ጥናት ባለሙያው አቶ ሞላ ሙጨ፣ የገበያ ልማት ትስስርና መረጃ ከፍተኛ ኦፊሰር አቶ መልካሙ ዘሪሁን፣ የግዥ ንብረት አስተዳደር የሥራ አስተባባሪ አቶ ጌትነት መረሳ፣ የፋይናንስ ኢኮኖሚ ልማት ጽሕፈት ቤት ሲኒየር የፋይናንስ ኦፊሰር አቶ ዳንኤል ታዬ፣ የግዥ ንብረት አስተዳደርና ጠቅላላ አገልግሎት ደጋፊ የሥራ ሒደት ወ/ሮ አስናቀች ዓለማየሁ፣ የግዥ ንብረት አስተዳደር የሒሳብ ሰነድ ያዥ አቶ ዮሐንስ አሰፋ፣ የዋና ሥራ አስፈጻሚ ጽሕፈት ቤት የክፍያና ሒሳብ ደጋፊ የሥራ ሒደት አስተባባሪ አቶ ፍቃዱ አንጫሞ፣ የንብረት አስተዳደርና ጠቅላላ አገልግሎት የግዥ የሥራ ሒደት ኃላፊ አቶ ግርማ ቶሎሳ፣ የአቅም ግንባታ ኃላፊ አቶ ጌታቸው ማሞ፣ የመሬት ልማትና ማኔጅመንት ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ ተገኝ ጦፋና የዋና ሥራ አስፈጻሚ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አቶ አምሳሉ ታደሰ ናቸው፡፡

ክሱን የመሠረተው የፌዴራል የሥነ ምግባርና የፀረ ሙስና ኮሚሽን ዓቃቤ ሕግ ሲሆን፣ በአራዳ ክፍለ ከተማ ወረዳ 3 ውስጥ የሚገኘው የኢዜድ አጠቃላይ ንግድ ሥራ አስኪያጅ አቶ ኢዮብ ዘነበ፣ በጉለሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 9 ውስጥ የሚገኘው የሱሳ ትሬዲንግ ሥራ አስኪያጅ አቶ ዮሐንስ ወንድሙና በየካ ክፍለ ከተማ ወረዳ 5 ውስጥ የሚገኘው የአጋዘወርቅ ጠቅላላ ቢዝነስ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበር ሥራ አስኪያጅ አቶ ደሳለኝ ወርቁ የተባሉ ግለሰቦችንም በክሱ አካቷቸዋል፡፡

ተጠርጣሪዎቹ ክስ የተመሠረተባቸው ክፍለ ከተማው ለአቅም ግንባታ፣ ለዋና ሥራ አስፈጻሚና መሬት ልማት ማኔጅመንት ጽሕፈት ቤት አገልግሎት የሚውሉ የቢሮ ዕቃዎች ለመግዛት የካቲት 11 ቀን 2006 ዓ.ም. በጋዜጣ ከወጣ የግልጽ ጨረታ ማስታወቂያ ጋር በተያያዘ መሆኑን ክሱ ያስረዳል፡፡

ተጠርጣሪ ሹሞቹ የቴክኒክ ኮሚቴና የጨረታ ኮሚቴ ሆነው ሲሠሩ፣ በአንድነት መንግሥትን ጐድተው ከላይ የተጠቀሱትን ሦስቱን ድርጅቶች ለመጥቀም በማሰብና በመተባበር፣ የክፍለ ከተማውን የግዥ መመርያ 3/2002 ሳይከተሉ፣ የዝርዝር ፍላጐት መግለጫ (Specification) ባልወጣላቸው የቢሮ ዕቃዎች ላይ ውድድር ማካሄዳቸውን ክሱ ይጠቁማል፡፡ በጨረታ ሰነዱ ላይ ከተቀመጠው ዝቅተኛ ዝርዝር መሥፈርት በታች (Minimum Standard Specification) መምረጣቸውን፣ በጨረታ ሰነዱ ላይ የተቀመጠውን ዝርዝር የፍላጐት መግለጫ አሻሽለው መረጣ ማካሄዳቸውን ክሱ ያብራራል፡፡

በጨረታ ሰነዱ ውስጥ ግዥ እንዲፈጸም ከተዘረዘሩ ዕቃዎች መካከል እያንዳንዱ ተጫራች ያቀረባቸው የቢሮ ዕቃዎች በምን ቴክኒካዊ ውጤትና የጥራት ደረጃ እንደወደቁ እንደማይታወቅ፣ በቅድመ ሁኔታ መቀመጥ የነበረበትን ዝርዝር የጥራት መሥፈርት ሲያስቀምጡ ፍትሐዊ ያልሆነ ውድድር በአቅራቢዎቹ መካከል ማድረጋቸውን ክሱ ያስረዳል፡፡ አቅራቢው ከገበያ ዋጋ በላይ ወስኖ ያቀረበላቸውን የቢሮ ዕቃዎች የቴክኒክ ኮሚቴው የዕቃ ጥራት ብቻ እንዳወዳደረ አስመስሎ፣ የጨረታ ኮሚቴው በአንድ ዋጋ ላይ ብቻ እንዲወስንና በጨረታ ኮሚቴው ግዥ እንዲፈጸም ማድረጋቸውንም ክሱ ይገልጻል፡፡

በአጠቃላይ ተጠርጣሪዎቹ የግዥ መመርያ 3/2002 መሠረት የማወዳደሪያ መሥፈርት አዘጋጅተው ማወዳደር ሲገባቸው፣ አቅራቢዎቹ በምን መሥፈርት እንደተመረጡ ግልጽ ባልሆነበትና የቴክኒክ ውድድር በሌለበት ሁኔታ ሕጋዊ አሠራሩን ወደ ጐን በመተው፣ በራሳቸው መንገድ የቴክኒክ ውድድር ማካሄዳቸውን ክሱ ያብራራል፡፡

የቴክኒክ ኮሚቴው ያለምንም የዝርዝር ፍላጎት መግለጫ የጨረታ ኮሚቴው ደግሞ ያለምንም የገበያ ጥናት በፈጸሙት ግዥ፣ በመንግሥት ላይ የ5,209,964 ብር ጉዳት እንዲደርስ ማድረጋቸው በክሱ ላይ ሰፍሯል፡፡

ተጠርጣሪዎቹ ክሱ ከደረሳቸው በኋላ ክሱን አይተውና ተገንዝበው ከሕግ አማካሪዎቻቸው ጋር ተነጋግረው ለመቅረብ ተለዋጭ ቀጠሮ ለጥቅምት 12 ቀን 2007 ዓ.ም. ተሰጥቷል፡፡

Source:: Ethiopian Reporter

bigwhy

የጊፍት ሪል ስቴት ባለቤት ታሰሩ

$
0
0

የጊፍት ሪል ስቴት ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር ባለቤትና ዋና ሥራአስኪያጅ አቶ ገብረየሱስ ኢተጋ በአዲስአበባ ከተማ አስተዳደር የሊዝ ቦርድ ከተፈቀደላቸው መሬት በላይ ይዘው በመገኘታቸው ተጠርጥረው በቁጥጥር ሥር ዋሉ።

gift አቶ ገብረየሱስ በቀድሞ ወረዳ 28 ልዩ ስሙ የካ አባጣፎ ተብሎ በሚታወቅ አካባቢ ከተረከቡት መሬት በተጨማሪ ከ30ሺ ካሬሜትር በላይ ይዘው በመገኘታቸውና እንዲያስረክቡም በተደጋጋሚ ቢጠየቁም ፈቃደኛ ሆነው ባለመገኘታቸው ከትላንት በስቲያ ሰኞ ዕለት በቁጥጥር ሥር ውለው ትላንት ፍ/ቤት መቅረባቸውን ምንጮቻችን ጠቁመዋል።

ምንጮቻችን እንዳመለከቱት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የሊዝ ቦርድ ለጊፍት ሪል ስቴት በቀድሞ ወረዳ 28 የካ ለገጣፎ አካባቢ የሚገኝ 13 ሄክታር መሬት ቦታ 21 ባለ 3 ፎቅ ኮንዶሚኒየም፣ 81 ቪላ ቤቶች፣ በመጀመሪያ ፌዝ ለመገንባት፣ 20 ኮንዶሚኒየም ሕንጻ እና 130 ቪላ ቤቶች መዝናኛ ሱቆችና ቢዝነስ ሴንተር ያለው ግንባታ በሁለተኛው ፌዝ ለመሥራት በሪል ስቴት መመሪያው መሠረት የሊዝ ዋጋውን ከፍሎ በሊዝ ቦርድ ቃለጉባዔ ቁጥር 4/97 በቀን 2/2/1997 እንዲወስዱ ተወስኗል። ሆኖም ጊፍት ሪል ስቴት የውል ማሻሻያ አድርገናል በማለት የመሬት መጠኑን አሳድጎ በሕገወጥ መንገድ ትርፍ መሬት መያዙን አስተዳደሩ አረጋግጧል። ይህንን ጉዳይ በቀድሞ አስተዳደሩ ከንቲባ አቶ ኩማ ደመቅሳ የሚመራው አስተዳደር ጥቆማ ቀርቦለት የካቲት 17 ቀን 2004 ዓ.ም በቃለ ጉባዔ ቁጥር 18/2004 ባካሄደው መደበኛ ስብሰባ ጊፍት ሪል ስቴት በሕገወጥ መንገድ የወሰደውን መሬት እንዲመልስ ወስኖ ክፍለ ከተማውም በእጁ የሚገኘውንም ካርታ እንዲያመክን ማዘዙን ምንጮቻችን አስታውሰዋል።

ጊፍት ሪል ስቴት በተደጋጋሚ ጉዳዩን አስመልክቶ ያቀረበው አቤቱታ አስተዳደሩ ሊቀበለው አልቻለም። በዚህ መሠረት በአቶ ድሪባ ኩማ የሚመራው አስተዳደር በ24/10/2006 በቁጥር አ.አ/ከጽ/03/7.7/390 በከንቲባ ጽ/ኃላፊ በአቶ አሰግድ ፊርማ በተፈረመ ደብዳቤ የሪልስቴቱ የአቤቱታ ጥያቄ ውድቅ መሆኑ ተገልጾለታል። ይህም ሆኖ ግን ጊፍት ሪል ስቴት ወደመሬት ባንክ እንዲገባ በተወሰነው ይዞታ ላይ ግንባታ በመጀመሩ የአስተዳደሩ ፍትህ ጽ/ቤት ከዓቃቤ ሕግ ጋር በመቀናጀት አቶ ገብረየሱስ ኢተጋ ሰኞ እለት በቁጥጥር ስር እንዲውሉ ከፍ/ቤት የመያዣ ትዕዛዝበማውጣት ግለሰቡን በቁጥጥር ስር በማድረግ ተባባሪዎችንም በመፈለግ ላይ እንደሚገኝ ታውቋል። አቶ ገብረየሱስ ትላንት በአዲስ አበባ ከተማ የካ ምድብ ችሎት ፍ/ቤት ቀርበው ፖሊስ ምርመራውን ለማጣራት የጠየቀውን የሰባት ቀናት ተጨማሪ ጊዜ ቀጠሮ እንደተፈቀደለት ለማወቅ ተችሏል።

ጊፍት ሪል ስቴት በሕገወጥ መንገድ ይዞታል የተባለው ይዞታ በወቅቱ የመሬት ሊዝ ጨረታ ከፍተኛ ዋጋ ሲሰላ ከ200 ሚሊየን ብር በላይ ግምት እንዳለው ምንጫችን ጠቁሟል።

ምንጭ፡ ዛሬ በአዲስ አበባ ታትሞ የወጣው ሰንደቅ ጋዜጣ

ጋዜጠኛ ውብሸት ታዬ ላልተወሰነ ጊዜ ወደ ቃሊቲ ተዛወረ

$
0
0

(ነገረ ኢትዮጵያ) በሽብርተኝነት ክስ ጥፋተኛ ነህ ተብሎ የአስራ አራት አመት እስር የተፈረደበት ጋዜጠኛ ውብሸት ታዬ በእስር ከሚገኝበት የዝዋይ እስር ቤት ላልተወሰነ ጊዜ ወደ ቃሊቲ ተዛወረ፡፡

Woubshet-Taye-Deputy-Editor-In-Chief-Awramba-Newspaper
የጋዜጠኛ ውብሸት ባለቤት ወ/ሮ ብርሃኔ ተስፋዬ ለነገረ ኢትዮጵያ እንደገለጸችው ውብሸት ከዝዋይ ወደ ቃሊቲ ከተዛወረ ቀናት ተቆጥረዋል፡፡ ‹‹ሆኖም ግን ብዙ ሰዎች ውብሸት ወደ ቃሊቲ መዛወሩን መረጃው የላቸውም›› ያለችው ወ/ሮ ብርሃኔ፣ ‹‹አሁን ውብሸት ቃሊቲ በፊት ለፊት በር በኩል ዋይታ ቤት በሚባለው በኩል ይገኛል፡፡ ከሰኞ እስከ አርብ ሙሉ ቀን ሊጠይቀው የፈቀደ ሁሉ መጠየቅ ይችላል›› ብላለች፡፡

ውብሸት ወደ ቃሊቲ የተዛወረበት ምክንያት የቤተሰብ ጉዳይ ስላለበት መሆኑን የጠቀሰችው ወ/ሮ ብርሃኔ ባለቤቷ ቃሊቲ የሚቆየው ላልተወሰነ ጊዜ መሆኑን ገልጻለች፡፡ ‹‹እስከ መቼ ቃሊቲ እንደሚቆይ ባላውቅም መስከረም 29 ቀጠሮ ስላለው እስከዚያው በዚሁ እንደሚቆይ እገምታለሁ›› ብላለች፡፡
ጋዜጠኛ ውብሸት የአንድ ልጅ አባት ሲሆን ቀደም ሲል ዝዋይ እስር ቤት እያለ ልጁን ለማየት ፈተና እንደነበር ለማወቅ ተችሏል፡፡ ‹‹አሁን ለጊዜውም ቢሆን ልጃችንን ይዠ ስለምጠይቀው ልጁን ቶሎ ቶሎ ማየት ችሏል›› ስትል ወ/ሮ ብርሃኔ ለነገረ ኢትዮጵያ ተናግራለች፡፡
የውብሸት ልጅ ፍትህ ውብሸት ይባላል፡፡ ይህ ህጻን ‹‹እኔም ሳድግ እንደ አባቴ እታሰራለሁ?›› ሲል መጠየቁ ይታወሳል፡፡

በሌላ በኩል ጋዜጠኛ ውብሸት ታዬ በእስር ቤት ሆኖ የጻፈው ‹‹የነጻነት ድምጾች›› መጽሐፍ ለንባብ መብቃቱን ባለቤቱ ወ/ሮ ብርሃኔ ገልጻለች፡፡

“ነጻነትነታችን እንደ ዕርዳታ እህል ከምዕራባውያን የሚለገሰን አይደለም!”

$
0
0

ለአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ በኢትዮጵያ ለሚገኙ የፖለቲካ መሪዎች ያስተላለፈው ግልጽ መልዕክት

የተወደዳችሁ በኢትዮጵያ የምትገኙ የፖለቲካ ፓርቲ መሪዎች፤

smneበቅድሚያ ለአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ (አኢጋን) የአክብሮት ሰላምታ በማቅረብ በትግሉ መስክ የምትከፍሉትን መስዋዕትነት የሚያደንቅ መሆኑን ይገልጻል፡፡ በተለይ በአሁኑ ጊዜ የፖለቲካ ምህዳሩ እጅግ ጠብቦ የለም የሚባልበት ደረጃ በደረሰበት ወቅት በምታገኙት ስንጥቅ ሁሉ እየተጠቀማችሁ ለህዝባችሁ የብርሃን ጭላንጭል ስለምትፈነጥቁ አኢጋን ሥራችሁን ያደንቃል፤ ያከብራል፡፡ እኛ በሥራችሁ ስኬት የምንመኘው ለቆማችሁለት የፖለቲካ ዓላማ ብቻ ሳይሆን ከህወሃት/ኢህአዴግ አገዛዝ ራሳቸውን ነጻ ለማውጣት አቅቷቸው መፈናፈኛ ላጡትም የመወሰን ኃይል እንደምትሰጧቸው በማመን ነው፡፡

አገራችን ካለችበት ወቅታዊ ሁኔታ አኳያ የበርካታዎች ጥያቄ “ህወሃት/ኢህአዴግን በምን ዓይነት የተሻለ አስተዳደር እንዴት መለወጥ ይቻላል የሚለው ነው?” ይህ ጥያቄ “እኛ ኢትዮጵያውያን የዘርና የጎሣ ትንንሽ አጥሮቻንን አፍርሰን ሁሉን አቀፍ ትግል ለማድረግ ተዘጋጅተናል ወይ?” ብለን ራሳችንን መልሰን አንድንጠይቅ የሚያደርገን ነው፡፡ እንዲሁም ከጎሣ ይልቅ ለሰብዓዊነት ቅድሚያ በመስጠት ሁሉም ነጻ ሳይወጣ ራሳችንን ነጻ ለማውጣት እንችላለን ወይ? ብለንም እንድንጠይቅ የሚያስገድደን ነው፡፡ …

ሽንፈት ላይ እያተኮሩና የጠላትን ኃይለኛነት እየሰበኩ ድል አይገኝም፡፡ ልዩነትን እያራመዱ ኅብረትና አንድነት ተግባራዊ መሆን አይችልም፡፡ ለአገራዊ ዕርቅ እንሰራለን እያሉ በፓርቲ መካከል ከዚያም በታች በግለሰብ ደረጃ መተራረቅ ካልተቻለ ብሔራዊ ዕርቅ ከቀን ቅዠት አያልፍም፡፡ እያንዳንዳችሁ የፖለቲካ ፓርቲዎች መድረክ፣ መኢአድ፣ አንድነት፣ ሰማያዊ፣ ኦህኮ፣ አረና፣ እና ሌሎች እጅግ በርካታ ፓርቲዎች የተቋቋማችሁትና ዓላማ ያደረጋችሁት ኢህአዴግን እየተቃወማችሁ ለመኖር እንዳልሆነ የፓርቲ ፕሮግራማችሁ ይመሰክራል፡፡ ወይም ዓላማችሁ የራሳችሁን የፓርቲ ምርጫ የማድረግና ፕሬዚዳንት (ሊቀመንበር)፣ ምክትል፣ ሥራ አስፈጻሚ፣ … በመምረጥ አዙሪት ውስጥ ራሳችሁን ላለማሽከርከር እንደሆነ ከማንም በላይ ራሳችሁ ታውቁታላችሁ፡፡ ከዚህ አንጻር በጥንቃቄና በብዙ ጥናት የተቀመጠው የፓርቲያችሁ ፕሮግራምና ዓላማ ለአገራችን አንዳች ለውጥ ሳያመጣ እንደዚሁ እንዳማረበት ቢቀመጥ ለሕዝብ የሚያመጣው ትርፍ ምንድርነው? እናንተንስ ለመቃወም ብቻ የምትሰሩ አያደርጋችሁምን? …… (ሙሉውን መልዕክት ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ)

Viewing all 15006 articles
Browse latest View live