Quantcast
Channel: Ethiopian News | ዘ-ሐበሻ | Latest News Provider | News For All
Viewing all 15006 articles
Browse latest View live

“ጉድ በል ጎጃም አለ ያገሬ ሰው!” የወያኔኢሕአዴግ ተላላኪው የዳላሱ ወጣት ኢብራሂም ሲራጅ ማን ነው?

$
0
0

በሚሊዮን ኢትዮጵያ(ከዳላስ)

dallas1ወያኔ/ኢሕአዴግ በውጭ ሃገር የሚኖሩት ኢትዮጵያውያንን ለማደራጀት የሚያስችላቸውን የጥፋት ውጥን በመወጠን ከተለያዩ የኢትዮጵያ ክፍል ተወልደውያደጉ ለሆዳቸው ያደሩ አደርባዮችን በመመልመል የቤት ስራውን እየሰራ ይገኛል። አያሌ ኢትዮጵያውያን የስርአቱን አስከፊነት በመገንዘብ ሳይወዱ በግድ የሚወዱት ሃደራቸውና ሕዝባቸውን ትተው ቢሰደዱም እንኳን  እስካሉበት የስደት  ሃገር በመከተል የከፋፍለህ ግዛ መሰሪ ፖሊሲያቸውን ለማስፈጸም በፖሊሲ ደረጃ በመንደፍ የጥፋት ተግባራቸውን ገፍተውበታል። በዚህም መሰረት ምንም እንኳን እዚህ ገቡ የሚባሉ ቁጥር ያላቸው አባላት ማፍራት ባይችሉም ጥቂት ርካሽ ተውዳጅነት ለማትረፍና የግል ንዋይ ፈላጎታቸውን ለማሟላት ከመራሹ መንግስት ጋር በመተባበር ህዝብን ለማወናበድና ለማታለል የሚተጉ ግን አልጠፉም።  ኢብራሂም ሲራጅ ከእነዚህ በጥቅም ከተደለሉትና የመሰሪው የወያኔ መንግስት ተልእኮ ለመወጣት ሌት ተቀን ደፋ ቀና ከሚሉት አንዱ ነው።

ዳላስ በወያኔ መሰሪ ተባባሪዎች እጅ ወድቃለች ማለት ባይቻልም እነዚህ ጥቂት ርዝራዦት በኮሚኒቲ፣ በቤተክረስቲያንና በሌሎችም ኢትይጵያዊ በሆኑት ተቓማት እጃቸውን በማስገባት ቀላል የማይባል የጥፋት ተልዕኮአቸውን ለመወጣት ሌት ተቀን ደፋ ቀና እያሉ ለቱባ የወያኔ አለቆቻቸው ታማኝ ለመሆን ተግተው ይሰራሉ። ምንም እንኳን በኢትዮጵያ የቁርጥ ቀን ልጆች አላማቸውን ማሳካት ባይችሉም። የጥፋቱ ሰለባ ከሆኑት ኢትዮጵያዊ ተቓማት ውስጥ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ደብረ ምህረት ቅዱስ ሚካኤል ካቴድራል ቤተክርስቲያንና (http://www.stmichaeleoc.org/) በዳላስ የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ የጋራ መረዳጃ ማህበር (http://maaecdallas.org/) ዋና ተጠቃሽ ናቸው። በእነ አቶ ተፈራወርቅ (ጋሻው ኢንሹራንስ) የሚመራው የጥፋት ቡድን አማካኝነት ቤተክርቲያኒቷን ፍርድ ቤት ሶስት ጊዜ በመክሰስ በሺዎች የሚቆጠሩ ዶላሮች ወጪ ዳርገዋል። ኮሚኒቲውም ምርጫ በመጣ ቁጥር የወያኔ ጀሌዎቻቸውን ለማስረጽ ህዝብን በማወናበድ ላይ ይገኛሉ። ከወራት በኳላ የሚደረገውን የመራዳጃው ማህበር የቦርድ አባላት ምርጫ ላይ የወያኔ አባላትን ለማስገባት ተጽዕኖ ለመፍጠር የቤት ስራቸውን እየሰሩ ናቸው። ይህ እውነታ ግንዛቤ ውስጥ በማስገባት ሁሉም የኮሚኒቲው አባላት ኮሚኒቲው በወያኔ እጅ እንዳይወድቅ ንቁ ተሳትፎ በማድረግ ሊታደገው ይገባል።

እነዚህ የጥፋት ሃይሎች እራሳቸውን “ሰበቡ” የሚል ስያሜ በመስጠት በእነ ተኮላ፣ ደምመላሽ፣ ተፈራወርቅና ሌሎችም መሪ ተዋናይነት የሚመራ ሲሆን ሁሌም ምክንያት እየፈጠሩ ከኢትዮጵያ ሕዝብ ጉሮሮ በተነጠቀ በወያኔ በተመደበላቸው ባጀት ስጋዊ ፍላጎታቸውን የሚያስደስቱ ለሌላው ግድ የሌላቸው ህሊናቸው የሸጡ አገርና ሕዝብን የካዱ የግል ጥቅማቸውን ብቻ የሚያዩ ስንስቦች ናቸው። የማህበሩ አባላት ለሚሰሩት የጥፋት ተልዕኮ ከገንዘብ ድጋፍ በተጨማሪ በትውልድ ቀዬያቸው በህገ ወጥ መንገድ ከድሃው ምስኪን የሃገሬ ገበሬ መሬት እየተነጠቀ ለውለታቸው የመኖሪያና የንግድ ቦታ መስሪያ ይሰጣቸዋል። ኢብራሂም ሲራጅ የዚህ ማህበር ተላላኪ እንደመሆኑ መጠን የጽዋው ተቓዳሽ በመሆን በባህር ዳር ከተማ ሲኒማ ቤት መስሪያ ቦታ ለውለታው ተችሮታል። እነዚህ የጥፋት ሃይሎች ኢትዮጵያውያን በሚሳተፉበትና የገቢ ማሰባሰቢያ ቦታዎችን በመገኘት ወያኔኢሕአዴግ ለዚህ ተግባር በተመደበውብ ባጀት በመለገስ ሕዝብን ለማወናበድና የኮሚኒቲው ተቆርቓሪ ለመምሰል ይጥራሉ።

የእድገትና ትራንስፎርሜሽን ፕላን(GTP) በተመለከተ የወያኔ/ኢሕአዴግ ቱባ ባለስልጣናት ወደ ሰሜን አሜሪካ በመጡበት ወቅት ምንም እንኳን ጥሪው ለሁሉም ኢትዮጵያውያን የሚመለከት ቢሆንም ሁሉም ኢትዮጵያዊ ለመታደም ግን አልታደሉም። ስብሰባው ለመታደም የተዘጋጀበት ስፍራ ብሄድም ውይይቱን ለመካፈል ከተነፈጉት አንዱ ነኝ። የኢትዮጵያ ጉዳይ የሁሉም እንጂ የወያኔ አባላት ብቻ አለመሆኑን እይርታወቅ ስብሰባውን ለጥቂት አባሎቻቸው ብቻ በደብዳቤ በመጥራት ሐገር ወዳድ ኢትዮጵያውያን ደብዳቤ የላች ሁም በማለት ወደ ስብሰባ አዳራሹ እንዳይገቡ ተደርገው በፖሊስ እንዲባረሩ ተደርገዋል። በዚህ ወቅት እንዳይገቡ የተደረጉ ሃገር ወዳድ ኢትዮጵያውያን ተቃውሞ ሲያሰሙ ለወያኔ የደህንነት አባላት የሚላክ ቪዲዮ በመቅረጽና ተቃውሞ እያሰሙ በነበሩት በመሳለቅ ኢብራኢም ሲራጅ ለወያኔ ታማኝነቱን አሳይቷል። ይህ ደግሞ ከሃገርና ህዝብ ክህደት በተጨማሪ ለዲያፖራው ማህበራሰብ ያለው ንቀት ምን ያህል እንደ ሆነ ያሳያል።

ኢብራሂም ሲራጅ በሰሜን አሜሪካ ስፖርት ፌደሬሽን(ESFNA) ዳላስን ወክለው ከሚጫወቱት ሁለት የስፖርት ክለቦች አንዱ በሆነው ኢትዮ ዳላስ ውስጥ እስከ ዛሬ ድረስ ላለፉት 11 አመታት ስጫወት ነበር ብሎ በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን የሰጠው ቃለ መጠየቅ በፍጹም ከውነት የራቀ መሆኑን ቡድኑ ውስጥ ከሚጫወቱት አባላት ለመረዳት ችያለሁ። ለነገሩ መች ኢቲቪ እውነት አውርቶ ያውቅና። ወያኔ ማለት የውሸት ከረጢት መሆኑን ከታወቀ ውሎ ሰንብቷል። ነገር ግን ቡድኑ አባላት ውስጥ በተፈጠረው አለመግባባት እጁን በማስገባት ከጀርባ በመሆን ለሁለት እንዲከፈሉና ልዩነታቸው በሰላም እንዳይፈቱ እንቅስቃሴ ሲያደርግ ቆይቷል። ወጣቶቹ ችግራቸውን በሰላማዊ መንገድ እንዲፈቱ ከማድረግ ይልቅ ከዋናው ቡድን እራሳቸውን ላገለሉት አባላት የቅርብ ጓደኞቹና ዘመዶቹ በመመልመል የጥፋት ሴራውን ሲሸርብ ነበር። ምንም እንኳን ያሰበው አላማ ባይሳካለትም የመጨረሻ ግቡ ግን ወጣቶቹን በጥቅም በመደለል የዛሬ ሁለት አመት ገደማ በአብነት ገመስቀል መሪ ተዋናይነትና በሼክ መሐመድ ሁሴን አል አሙዲን ሙሉ የገንዘብ ድጋፍ ለተቓቓመው የስፖርት ማህበር ለማስረከብ ነበር።

ኢብራሂም ሲራጅ በአሁን ሰአት ኢትዮጵያ የሚገኝ ሲሆን በኢትዮጵያ ቴሌቪሽን በእንግዳ ፓሮግራም በተደረገለት ቃለመጠየቅ ኢትዮጵያ ውስጥ የማይካድ ለውጥ አለ፣ በውጭ ኃገር የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ስለ ልማቱ የሚናገሩትን አልሰማም፣ ወያኔኢሕአዴግ በሚያደርጋቸው ሁሉም ስብሰባዎች መሪ ተዋናይ ነኝ፣ የፖንድ ሽያጭና በቅርብ የማውቃቸው አቅም ያላቸው ኌደኞቼን በማስተባበር ላይ ግንባር ቀደም ነኝ ይለናል። በዚህም አንባገኑ የወያኔ ስርአትን ቀንደኛ ደጋፊ መሆኑና መራሹ ወያኔ ልማታዊነት ምስክርነት ይሰጣል። ውሸታሙን ኢቲቪንና ወያኔን እውነትነት አስረግጦ በመናገር የዲያስፖራውን ማህበረሰብ ውሸታም መሆኑን ይነግረናል። ይህ ደግሞ ለዲያስፖራው ማህበረሰብ ያለው ንቀት ያሳያል። የኢትዮጵያ ሕዝብ በአንባገነኑ ስርአት ለእስራት፣ ለስደት፣ ለሞት፣ ለረሃብ፣ ለእንግልትና ለስቃይ እየተዳረገ ባለበት ሁኔታ ወያኔን ማሞካሸትና ልማታዊነት መመስከር የህሊና ዳኝነት የጎደለው ከመሆን ውጪ ምን ይሉታል። ለመሆኑ ወያኔ የሚለውን የሚያስተጋባለትን እንጂ መች ሕሊና ያለው ሰው ይፈልግና።

ጀግናው በላይ ዘለቀ ያፈለቀችው ጎጃም ኢብራሂም ሲራጅ አሳድጋለች የናት ሆድ ዥንጉርጉር ይሉታል ይህ ነው። አንዱ የባህርዳር አንድ ክለብ የሚያሰነጥለው አብሮ አደጉ ስለ ኢብራሂም ሲራጅ ሲናገር ይህ ትልቅ ሃብታችን ነው ልንጠቀምበት ይገባል ብሎናል። ጀግናው በላይ ዘለቀ በተወለደበት ሃገር ሃገሩን ሽጦ ለሆዱ ያደረውን እንደ ሃብት ሲቆጠር ጉድ በል ጎጃም ማለት ይሄኔ ነው።

ውድ የሐገሬ ልጆች ሆይ ኢትዮጵያ ሃገራችን አንድነቷና ዳርድንበሯ ጠብቃ ልትቆይ የቻለችው ብዙ የደም መስዋዕትነት ተከፍሎባት እንድሆነ ሁሉም ጠንቀቆ የሚያውቀው ስለሆነ እኔ ልነግራች ሁ አልሻም ለቀባሪ ማርዳት እንዳይሆንብኝ። ዛሬ ግን ወያኔና ግብራበሮቹ ይህን ታሪክ ለማጥፋት የዘር ፖለቲካ በመከተል ህዝቡን አንድነቱን እንዳይጠብቅ በማድረግ፣ የገዛ መሬታችን ለጎረቤት ሀገራት አሳለፎ በመስጠት፣ ምስኪን ገበሬ በማፈናቀል ለውጭ ባለሃብት በመሽጥና ሌሎችም አያሌ መሰሪ ተግባራቸውን ገፍተውበታል። ወያኔ/ኢሕአዴግ ያለ ሕዝብ መልካም ፍቃድ ስልጣን በአፈሙዝ በማስፈራራት ቢቆናጠጥም ሕዝብ ያለመረጠው መንድስት ዘላቂነት ሊኖረው ስለማይችል ሰርጎገብ ከሆኑት የወያኔ ተላላኪዎች ሰላባ እንዳንሆን ነቅተን በመጠበቅ ማጋለጥ ይኖርብናል። የዚህ ጽሁፍም ዋናው አላማም ይህ ነው።

ኢብራሂም ሲራጅ በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን የእንግዳ ፕሮግራም ያደረገው ቃለመጠይቅ እዚህ በመጫን ይመልከቱ! http://www.diretube.com/engeda/ebrahim-serag

አንድ ሕዝብ!!!

አንድ ኢትዮጵያ!!!

ኢትዮጵያ ለዘላለም አንድነቷን ጠብቃ ትኑር!!!


ጋዜጠኛ ታዲዮስ ጌታሁንም ተሰደደ

$
0
0

journalist getahun(ዘ-ሐበሻ) የሎሚ መጽሔት ማኔጂንግ ኤዲተር ጋዜጠኛ ታዲዮስ ጌታሁን ከሀገር ተሰደደ። ማክሰኞ ነሐሴ 21 /2006 ዓ.ም በኢትዮጵያ አየር መንገድ ለመውጣት ሲል በሀገር ውስጥ የደህንነት ኃይሎች ተይዞ ታስሮ የነበረ ሲሆን ነሐሴ 28 ቀን 2006 ዓ.ም ከሀገር መሰደዱ ተረጋግጧል።

መንግስት የግሉ ፕሬስ ጋዜጠኞችን በከፍተኛ ሁኔታ እያሳደደ ባለበት በአሁኑ ወቅት የሎሚ ፣የጃኖ ፣የአዲስ ጉዳይ፣የእንቁና የአፍሮ ታይምስ አሳታሚዎችን ጨምሮ አንድ ወር ባልሞላ ጊዜ ውስጥ 15 ጋዜጠኞች ከሀገር ተሰደዋል ።

መንግስትን ከምቃወምባቸው ምክንያቶች 2ኛው: * የግማሽ ሚሊዮን ኮንትራት ሰራተኞች አበሳ በሳዑዲ አረቢያ

$
0
0

Saudi arabia ethiopia 1

Saudi arabia ethiopia 2

Saudi arabia ethiopia 3

Saudi arabia ethiopia 4
ከነብዩ ሲራክ (ሳዑዲ አረቢያ)

* የግማሽ ሚሊዮን ኮንትራት ሰራተኞች አበሳ … !

ህገ ወጡ የስደት መንገድ ይቆም ዘንድ በሚል እሳቤ የኢትዮጵያ መንግስት የሳውዲ አረቢያ የኮንትራት ሰራተኛ ማቅረብን ተስማሙ ተባለ። ስለተደረገው ስምምነት ውል ግን የሚታወቅ ነገር ጠፋ ። ከሁለትዮሽ ስምምነት የወጣ ውል ነው ተብሎ በሚታወቀው የተሸፋፈነ ስምምነት ከግማሽ ሚሊዮን በላይ የኮንትራት ስራተኞች ወደ ሳውዲ ገቡ።

ህጋዊ ፈቃድ ይዘው በህጋዊ መንገድ የሰሩ ባይጠፉም በ”ህጋዊ ” ፍቃድ ስር የኮንትራት ሰራተኞች ከማገናኘት ጀምሮ እስከ ሰራተኛ አቅርቦት ህገ ወጥ አካሄድ ተቀይጦበት ዜጎች በቂ መረጃ ወደ ሌላቸው ሳውዲ የገጠር ከተሞች ሳይቀር ማሰራጨቱ በርትቶ ቀጠለ ። ኤጀንሲዎች በየገጠሩ የደላላ ቡድን በማሰማራት ለአቅመ አዳም ያልደረሱ ፣ በቋንቋ ከራሳቸው ዜጋ እንኳን መግባባት የማይችሉ ፣ ፊደል ያልቆጠሩ የሚባሉትን ጨምሮ፣ ለቤት መብራት እና ለመኪና እንግዳ የሆኑትን እህቶች በቀቢጸ ተስፋ እያማለሉ በተጭበረበረ መንገድ እንደላኳቸው መረጃዎች በስፋት ተገኙ። በኮንትራት አጠቃላይ ወጩ በቀጣሪው የሚከወን ቢሆንም ጉዳዩን ማስጨረሻ፣ የቲኬት እና ሌላ ሌላ ወጭ እየተባለ አራጣ ብድር ሳይቀር ለከፍተኛ ተዳርገው ስደቱን እንደተቀላቀሉ በግንባር ያገኘኋቸው ተገፊዎች ቅስማቸው በሃዘን ተሰብሮ እያነቡ ምሬታቸውን ገልጸውኛል !

ይህ ሁሉ የሆነው በመንግስት በኩል ምንም አይነት ቅድመ ዝግጅት ፣ ስልጠናና የማስተባበር ስራ ሳይሰራ ነበርና ወደ ሳውዲ የመጡት ኮንትራት ሰራተኞች መዳረሻቸውን እንኳ በትክክል የሚከታተልና የሚመዘግብ ተወካይ አልተዘጋጀም። ይህም ብዙ ሳይቆይ አደጋ አስከተለ …ከዚያ በኋላ የሆነውን ማንሳት ይከብዳል ! “…ገደሉ ፣ ተገደሉ ፣ ሞተው ተገኙ ፣ ራሳቸውን ሰቀሉ ፣ ከፎቅ ተወረወሩ፣ ተደፈሩ ፣ አበዱ ፣ ሰው አሳበዱ ፣ በየአውራ ጎዳናው ተንከራተቱ ፣ ወድቀው ታዩ …” ወዘተረፈ ተብሎ …ሰቅጣጭ መርዶ ጆሯችን እየከበደው መስማት ግድ አለው !

ህጋዊ ሽፋን የያዙ የሃገር ቤት ደላሎች ፣ አሸጋጋሪዎች ብቻ ሳይሆን መንግስት መስሪያ ቤት ተቋማት ፣ ከቀበሌና ወረዳ እስከ ማህበራዊና የኢሚግሬሽንና ደህንነት መረጃን ሳያረጋግጡ በመስጠታቸው በአብዛኛው እህቶቻችን ለዚሀ የከፋ አደጋ ተጋለጡ ። ለሁሉም የሚያም የሚያሳዝነው ይህ ስህተት ተሰርቶ የተሰደዱ ወገኖች ባሉበት ሃገር የቅርብ ርቀት በጅዳ የኢትየጵያ መንግስት የቆንስል ፣ በሪያድ የኢንባሲ መ/ቤት ቢኖሩም ዜጎች ሰብአዊ መብታቸው ሲጣስ ለመብታቸው መከበር አይተጉላቸውም !
እናም መብታችን የሚያስከብር አጥተን ቀኑ እንደጨለመብን እየተገፋን አመታትን ገፍተናል !

መንግስት ሆይ ስማን !
ነቢዩ ሲራክ

ጅራፍ ራሷ ገርፋ ራሷ ትጮሃለች (አስገደ ገ/ስላሴ ወ/ሚካኤል)

$
0
0

‹‹ብርሃኑ በርሄ የህወሓት አባል ነው›› 
አስገደ ገ/ስላሴ ወ/ሚካኤል (ከመቀሌ)

 

አስገደ ገ/ስላሴ ወ/ሚካኤል

አስገደ ገ/ስላሴ ወ/ሚካኤል

የአረና ሊቀ መንበርና ሌሎች አመራሮች ባለፈው ሃምሌ 18-20/2006 ዓ.ም በተካሄደው መደበኛ የማ/ኮሚቴ ስብሰባ በጠንካራ አባላቱና አመራሮች በተወሰደው ህገ- ወጥ እርምጃ ጥፋታቸውን ለመሸፈን በተለያዩ ጋዜጦች፣ መፅሄቶችና ማህበራዊ ድረ-ገፆች የስም ማጥፋት ዘመቻ ተዘምቶብን እንደሰነበተ የሚታወስ ነው። እኛም ግብረ መልስ ስንሰጥ ቆይተናል። አሁን ደግሞ የስም ማጥፋትና ውሸታም ተግባራቸው ቀይረው በሌላ መልክ ወንጀላቸውን ለመሸፈን እየሞከሩ ነው። 

መነሻየ በነገረ ኢትዮጵያ ጋዜጣ ነሃሴ 2/2006 የአረና ሊቀመንበር ብርሃኑ በርሄ በሰጠው ቃለ ምልልስ እኛን በተመለከተና አጠቃላይ የትግል ሂደቱን መሰረታዊ ስህተት በመሆኑ ዋና ዋና ነጥቦችን በመለየት መልስ ለመስጠት ተገድጄለሁ። 

ብርሃኑ በርሄ ‹‹ዴሞክራሲያዊ ያልሆነ ገዢው ፓርቲ በሰላማዊ መንገድ በምርጫ ውድድር ከስልጣኑ እንዲወርድ ማድረግ አልያም የመንግስት ስልጣን ባንይዝም የህዝብ ጥያቄና አጀንዳ የፖለቲካ ስራችን ማእከል በማድረግ ተገዶም ቢሆን መሻሻል እንዲያደርግ በመታገል ለውጥ እናመጣለን ብለን ነው የምናምነው›› ይላል። ብርሃኑ በርሄ የተወላዋይ ሃይሎች አስተሳሰብ እዚህ ሲጋለጥ፤ እኛ አረናዎች የምንታገለው አምባገነኑ የህወሃት ስርአት እናስወግዳለን ስንል በአይዶሎጂ በሁሉም አንድ አይነት ፖሊሲዎች በሰብአዊና ዲሞክራሲያዊ መብት አጠባበቅ ባለን መሰረታዊ ልዩነት ህወሓት ኢህአደግን በምርጫ በማስወገድ የስርአት ለውጥ ለማምጣት ነው። ብርሃኑ በርሄ ግን የህወሓት መሪዎች በሚፈልጉት አቅጣጫ እየተራመደ ‹‹እኛ ስህተት ካለን በውስጣችን ሁናችሁ አስተካክሉን ለጠባቦችና ትምክህተኞች አሳልፋችሁ አትስጡን›› የሚሉት አቋም የሚያራምድና ሁለተኛ ልደቱ ሁኖ በስመ ተቃውሞ እየሸወደን ይገኛል። 

ብርሃኑ: ‹‹አፈናው እጅግ መጠናከሩና የፋይናንስ አቅማችን ውስኑነት የሚፈጥሩት ጫና ካልሆነ በስተቀር ከህዝብ ድጋፍና ፖሊሲያችን ከማስተዋወቅ አንፃር በመጪው ምርጫ ሰፊ ሽፋን ሊኖረን ይችላል›› ይላል። ሙሽራ ሳይዙ ሚዜን ይቀጥራሉ እንደሚባለው የብርሃኑ መጪው ምርጫ ለማሸነፍ ወይስ ለመሸፈን? የህወሓት ተግባራት በማጋለጥ የራስህን ሃሳብ በግልፅ ለህዝብ በማሳመንና የህዝብን ማዕበል በመፍጠር ነው ማሸነፍ የሚቻለው። ብርሃኑ በርሄና ጓደኞችህ ግን በዘንድሮ አመት በ8 ከተሞች ህዝባዊ ስብሰባ ተጠርቶ በ6 ከተሞች ሲከሽፍ በቀሩት ከተሞች ጥቂት ከተሞች ነው ያገኘነው። የተሰራጩ የቅስቀሳ ፅሁፎችም የህዝቡ ችግር ነቅሰው የሚያወጡ ሳይሆኑ ለህወሓት መሪዎች ተገዢነትና የተለሳለሱ እንደውም የሚያሞካሹም ጭምር ነበሩ። በነዚህ እንቅስቃሴዎች ጥቂት አመራሮች እንደ አብርሃ ደስታና እኔ የመሳሰልን በጋዜጣ በፌስቡክ በሬድዮ የምናደርጋቸው ቅስቀሳዎችም በብርሃኑ በርሄና በአቶ ገብሩ አስራት ተቀባይነት አልነበራቸውም። ለዚሁ እንደ ማረጋገጫ ብርሃኑ በርሄ እኔ በነበርኩበት ለ5 ስራ አስፈፃሚ አባላት ሰብስቦ በሚዲያ የምትፅፉትና በሬድዮ የምትናገሩት ለህወሐት መሪዎችና ካድሬዎች የሚያናድድ መሆን የለበትም፡፡: ተናደው በኛ ላይ እርምጃ ሊወስዱብን ነው ብሎ በተለይ በኔና አብርሃ ደስታ በማነጣጠር ነው ሽብር የፈጠረብን። አቶ ገብሩ አስራትም ከ8 ወር በፊት አዲስ አበባ ላይ በተደረገው የስራ አስፈፃሚ ስብሰባ በጥያቄ መልክ ያነሳው ‹‹አብርሃ ደስታና ሌሎች የሚፅፉትና የሚናገሩት ከፖሊሳችንና ከመስመራችን ጋር አብሮ ይሄዳል ወይ እነዚሀ ሰዎች ቢቆጠቡ?›› ብሎ ተናግረዋል። በዛን ወቅት አብርሃ ደስታ ተናዶ ‹‹ይህ አባባል የግለሰቡን ነፃነት ይነጥቃል›› ብሎ መልስ ሰጥቶታል። 

በሌላ በኩልም የፋይናንስ እጥረት ካልወሰነን ብዙ ስራ እንሰራለን የሚለው የነበረው ገንዘብ መቸ አነሰና እድሜ ለደጋፊዎቻችንና‼ ግን ያ ገንዘብ በጥቂት የቡድን አመራሮች በብርሃኑና ሶስት ስላሴዎች ቁልፍ በመሆኑ የፋይናንስ ስርአታችን በጣም የተበላሸ ከመሆኑ በላይ ለሙስና የተጋለጠ ሁኖ ይገኛል። 

አረና በምርጫ ሰፊ ሽፋን እንዲኖረው ከተፈለገ ብርሃኑ በርሄም ሊቀ መንበር ሁኖ ከተደበቀ፤ እነ ገብሩ አስራትም አዲስ አበባ ምሽግ ከሰሩ፤ አባሉና ህዝቡ ማን ያንቀሳቅሰዋል? ብርሃኑ በርሄና የአረና ህዝብ ግኑኝነት ኃላፊ ተብየው አምዶም ገ/ስላሴ’ኮ ሌላው ቀርቶ ሚዲያዎች ስለ አብረሃ ደስታ መረጃ እንድትሰጧቸው ፈልገው በተደጋጋሚ ስትጠየቁ ፍቃደኞች አይደላችሁም፡፡ ለምሳሌ እንደ ማስረጃ ኢሳትን መጥቀስ ይቻላል። በምርጫ ብዙ ቦታዎች መሸፈን ይቻላል የምትለው የትኛው አባል ይዘህ ነው ምትሸፍነው? ከአለቆችህ በተሰጠህ ትእዛዝ’ኮ አባሉን በትነኸዋል። በየትኛው አቋምህ ጠባብ ፀረ-አንድነትና ውህደት የሆነ ጠባብ የህወሓት አስተሳሰብ ወርሰህ ሰፊ የኢትዮጵያን መሬት ምትሸፍነው? አሁንም ዜጎችን ባትሸውዱ‼

ብርሃኑ በርሄ፡ ‹‹በፓርቲው ችግር የለም ነገር ግን የሰዎች አቋም ባህሪም ጭምር በእንቅስቃሴው ፈተና ውስጥ ስለሚገቡ አንዱ ጠንከሮ ሲወጣ ሌላው አዳናቃፊ የሚሆንበት አጋጣሚ ይስተዋላል፤ እንቅስቃሴው ሲበረታና እንቅስቃሴውን ለማኮላሸት የሚሰነዘሩ ጥቃቶች ሲበዙና ሲከብዱ ተስፋ መቁረጥም የሚጠበቅ ነው፤ ሌላው ደግሞ እንቅስቃሴው የሚወልዳቸው ፈተናዎች ከብደውት ወይ ብዥታ አድሮበት የመቀዛቀዝና ግራ የመጋባት ባህሪ ይስተዋላል›› ይላል። 


በአረና ውስጥ ዋናው ችግር ፈጣሪዎች አንተና አለቆችህ ናችሁ፤ በ2002 እኮ አንተና እነ ገብሩ አስራት እንቅስቃሴያችን ከመቀሌና አከባቢዋ መራቅ የለብንም፤ ለሪስክ (አደጋ) እንጋለጣለን አላችሁን፤ እኛ ገፍተን እኮ ነው ትግራይን ከጫፍ እስከ ጫፍ ተንቀሳቅሰን 138 ጠንካራ አባላት ለውድድር ያቀረብነው፤ እነ አረጋዊ ገ/ዮሃንስ’ኮ እንደ ሰንጋ በሬ የታረደው በበረሃ ሲቀሰቅስ ነው፤ ትግሉ የከበደህ’ኮ አንተ ነህ፤ ከባድ ነው በምትለው አከባቢ’ኮ ተደብቀሃል፤ ሌላው እንተወውና ዘንድሮ በተደረገ እልህ አስጨራሽ ህዝባዊ ስብሰባዎች’ኮ በብዙ ቦታዎች ተደብቀሃል፤ የአኒማል ፋርም የአመራር ስልትህ በመከተል ችግር እየፈጠርክ ያለኸው’ኮ አንተ ነህ፤ ታድያ በየትኛው ሞራልህና ብቃትህ ነው አንተ “ተስፋ ቆርጠው የሚሸሹ አሉ” ማለት የምትችለው? ቁጥር አንድ ተስፋ አስቆራጭ አንተ መሆንህ እነዚህ በየግዜው ከፓርቲው የለቀቁ በሺ የሚቆጠሩና አሁን በፓርቲው ውስጥ ያሉም እየገለፁት የሚገኝ። ብርሃኑ ማን መሆንህ የትግራይ ህዝብ በተለይ የመቀሌ ህዝብ ያውቅሃል፤ የአድዋ፣ የአላማጣ፣ የአዲጉዶም፣ የውቅሮ፣ የማይጨውና ሌሎች አከባቢዎች’ኮ አቋምህ ከህወሓት ምንም ልዩነት እንደሌለህ ነግሮሃል።

ብርሃኑ በርሄ፡ ‹‹የአረና ከፍተኛ አመራር እነ አስራት አብርሃም ቡድናዊነት አለ ብለው ከፓርቲው መሸሻቸው በኔ እምነት ሃላፊነትን አለመወጣት ነው›› ይላል። እነ አስራት አብርሃም በፓርቲው ውስጥ የነበሩ ችግሮች አለመታገላቸው ከብርሃኑ እስማማለሁ። ነገር ግን ያሁኑ ወጣቶች ከዚያ ያረጀና ያፋጀ ፀረ-ዲሞክራሲ ትውልድ በቋንቋም በባህልና አስተሳሰብ አይግባቡም። እነ አስራት ብዙ ታግለዋል፤ በውስጣችን የነበሩ ችግሮችም ለመታገል ሞክረዋል፤ አንተ ስብሰባ ረግጠህ እስከምትወጣ፤ ምክንያት እየፈጠርክ ከስብሰባ ወጥተህ በግል ስራህ ትውል እንደነበርክ እናቃለን፤ ባንተና በ3ት ስላሴዎች ባህሪ ምክንያት እስካሁን እነ አስራትን ጨምሮ 18 ማ/ኮሚቴ፣ ስራ አስፈፃሚና ቁጥጥር ኮሚሽን ከፓርቲው አግልለዋል፤ ችግሩም አሳታፊነት የለም፣ አባታዊነት ነግሰዋል፣ የፋይናንስ ስርአታችን ግልፅነት የለም ወዘተ.በማለት ነው። እንድያው አንዳንዶቹ “የአረና አመራር በስም ካልሆነ ከህወሓት በምንም አይለይም” ብለው ላንተ የነገሩህ የአረና መስራች አባላት የነበሩ እጅግ ብዙ ናቸው። 

እነ አስራት አብርሃም በነበሩበት እኮ ቡድናዊነት እጅጉን የጠነከረ ነበር፤ ያ ቡድናዊነት በስራ አስፈፃሚ ውስጥ ከላይ እንደገለፅኩት አራታችሁ በድብቅ የጨረሳችሁት ጉዳይ ወደ ስራ አስፈፃሚና ማ/ኮሚቴ የሚቀርበው ለይስሙላ ነበር፤ ማ/ኮሚቴ ለስሙ የተቀመጠ እንጂ አምስት አመት ሙሉ የሰራውና የሚያውቀው አልነበረም፤ ያ ቡድናዊነት አሁንም ተባብሰዋል።
ብርሃኑ በርሄ፡- ‹‹እነ አስራት በለቀቁት ማግስት በተካሄደው 3ኛ ድርጅታዊ ጉባኤ ቡድናዊነት እንዳለ አስመስለው ሲናገሩ የነበሩ ግለሰዎችም አላሳመኑም ብቻ ሳይሆን ለስሙም አላነሱም፤ ስለዚህ እነ አስራትም ሆነ አስገደ የሚያማርሩት ቡድናዊነት አረና ውስጥ አልነበረም›› ይላል፡፡ ሀሰት ተደጋግሞ ሲነገር ሃቅ ይሆናል የሚል የነ ሂትለር፣ መንግስቱና ህወሓት ብሂል ይዘህ የትም አትደርስም። ከ3ኛ ጉባኤ በፊት በ3ት የስራ አስፈፃሚና በ2ት ማ/ኮሚቴ መደበኛ አመታዊ ስብሰባ ተነስተዋል፤ የፋይናንስ ስርአታችን በም/ሊቀመንበርና በ3ት ስላሴዎች በሚስጥርና በቡድናዊነት መሆን የለበትም፤ ወደ ስብሰባ የሚቀርብ አጀንዳ በህገ ደንብ መሰረት ሳይሆን በጥቂት ስራ አስፈፃሚ በቡድናዊነት መሆን የለበትም፤ የዲፕሎማሲ ስራዎች ለወጣት አመራሮች እድሉን አለመስጠት ወዘተ የሚሉ ወሳኝ ጥያቄዎች ተነስተዋል። የዚህ ቡድናዊነት እንደ ማስረጃ ደግሞ በ3ኛ ጉባኤ ታይቷል፤ የጉባኤው ተሳታፊዎች አባላት መሆናቸውና አለመሆናቸው ማይታወቁ፤ በጉባኤው ጠንካራ ነባር አባላት ወደ አመራር እንዳይመጡ አስቀድሞ በህዝብ ግኑኝነትና የድርጅት ጉዳይ ሃላፊዎች የማያውቁት ባወቁ ጊዜም የተቃወሙት አቶ ብርሃኑና 3ት ስላሴዎች ያወጡት ካሪክለም የውሸት ስልጠና የሰጥቷቸው ለጉባኤ የቀረቡ መሆናቸው ሁሉም አባል ያውቃል። ሌላው ቀርቶ በጉባኤ ብርሃኑና 3ት ስላሴዎች በየ6ት ሰአት በድብቅ እየተሰበሰቡ ይወስኑት እንደነበር ፤ከዚያም አልፈው የፕሮዚዴሙ ለቀመንበር አብርሃ ደስታም ወደ ቡድኑ በማስገባት በማስፈራራት ጉባኤው በድፈን ድፈን እንዲታለፍ ተደርጓል። በተለይ ደግሞ በውህደት ጉዳይ፣በፌደራሊዝም፣ በመሬት ጉዳይ፣ ህገ-ደንብን ማሻሻል በተመለከተ ጊዜ ስሌለለን የሚመረጠው ማ/ኮሚቴ አይቶ እንዲወስን አድርግ ብለው ጉባኤተኛ እንዲታፈን እንዳደረጉ አብርሃ ደስታና ስልጣኑ ሕሸ የሚመሰክሩት ነው። በተለይ ገብሩ አስራትና አረጋሽ አዳነ የፕሮዚዴም አባላት ስለነበሩ አብርሃ ደስታን ያስፈራሩት ነበር። ብርሃኑ በርሄ በአረና ቡድናዊነት አልነበረም፣ አሁን ደግሞ ቡድናዊነት የሚል ሃሜት ወደ አባታዊነት ተሸጋገረ። 

በአረና አባታዊነትና አምባገነንነትን በሚመለከት በየካቲት 2005 መደበኛ ማ/ኮሚቴ ስብሰባ እኔ አንስቼው ተሰብሳቢው ጠንከር ብሎ ለብርሃኑ በርሄ ሂስ በመሰነዘሩ ብርሃኑ አባታዊ በሆነ ትእቢት በተሞላበት በንቀት መድረክ ረግጦ ወጥቶ በኋላ ተለምኖ ነበር የተመለሰው። ሌላ የአባታዊነት መገለጫ በአረና ስራ አስፈፃሚ ስብሰባ የፋይናንስ አቅማችንና አሰራራችን ለሁሉም ስራ አስፈጻሚ ግልፅ ይሁን የሚል ጥያቄ ቀርቦ በአቶ አውዓሎም ወልዱ የፋይናንስ አቅማችን ሁሉ የስራ አስፈጻሚ አባል ሊያውቀው ግዴታ አይደለም የሚል ሃሳብ ሲሰነዝር ገብሩ አስራት ተቀብሎት አረጋሽም ጨምራበት በዛው አለፈ፤ ታዲያ ከዚህ በላይ አባታዊነት ምን አለ? ከፓርቲዎች የሚደረገው ግንኙነት በቡድንነት እንደሆነ ሲነገራቸው ያኮርፋሉ፤ ሁሉም ነገር እኛ እንጨርሰው በማለት አያሳትፉም ሌላ አባል ከሰራ እንደሚያበላሽ አድርገው ነው የሚያዩት፤ ሌላው ቀርቶ ግለ ሰዎች ገዢው ፓርቲን በማጋለጥ በሚዲያ የምንሰነዝረው ሃሳብ መጀመርያ ኢዲት እናድርገው ብለውናል ተቀባይነት ባያገኙም፤ ታዲያ የግለሰብ መብት መጣስ የለበትም የሚለው የአረና እምነት አይፃረርም?

በሌላ በኩል ወደ ውጭ የዲፕሎማሲያዊ ስራ ከወጣቶች እንላክ ስንል በነዚህ 4ቱ ሰዎች ተቀባይነት አላገኘም፤ ወጣቱ ምንም አይሰራም ያበላሻል’ጂ የሚል አመለካከት ነበር፤ በሃገር ውስጥም ስለ ውህደት የት ደረሰ ተብለው ሲጠየቁ ለሁሉም ነገር በሚስጥር ይዘውት ነበር፤ በመጨረሻ ከአንድነትና ሌሎች የአማራ ፓርቲዎች አንዋሃድም ሊውጡን ነው ብለውናል፤ እንደውም በዚህ በሃምሌ 19ና 20/2006 የማ/ኮሚቴ ስብሰባ በ3ት አቅጣጫ ጦርነት ተከፍቶብናል፤ 

1. በህወሓት 2. በበተቃዋሚ ፓርቲዎች 3. በውስጣችን ባሉ በጥባጮች በማለት እኛን ካባረሩ በኋላ ያወጡት መግለጫ ያሳያል። ይህንን ደግሞ ለምን ተነካን ብለው ያላቸው አባታዊነት አሳይተዋል። 

ብርሃኑ በርሄ ‹‹በአረና የመብት ጥያቄ አንስቶ የታፈነ አንድም የለም፤ ታፍነናል በማለት ለሃገር ውስጥና ለውጭ ሚዲያዎች ብቻ ሳይሆን ለማይመለከታቸው ፓርቲዎች ሳይቀር የዚህ አመት አስገራሚ ሊባል የሚችል ምርጥ ውሸት በመደርደር የፓርቲያችንና አመራሩ መልካም ስም ለማጥፋት የዘመቱ›› ይላል፡፡ ደግ ብርሃኑ ለማያውቀው ሰው ሲናገር ሃቅ መስሎ ሊሰማው ይችላል። ሃቁን ለመናገር ግን ካሁን በፊት ለመግለፅ እንደሞከርኩት በአረና ትግራይ ዲሞክራሲያውነት መስፈርት ብለን የምናምንበት ከግለሰው መብት እስከ ቡድንና የህዝቦች መብት መከበር ነው፤ በብርሃኑና ጓደኞቹ አመለካከት ግን የግለሰው መብት አያከብሩም ብቻ ሳይሆን በግልም ሆነ በቡድን ማንኛውም አይነት ጥያቄ ማስነሳት ወንጀል ነው፤ ለዚሁ ምስክር በተለያዩ ጊዝያት ጥያቄ በማንሳታቸው በመታፈኑ ከፓርቲው ራሳቸው ያገለሉ ግን ደግሞ በህወሓትነት የተፈረጁ ግን እስካሁን ከህወሓት ምንም ግንኙነት የሌላቸው አሉ፡፡

አሁን የተባረርን አባላትና አመራርም በፓርቲው ያሉ ነባራዊ ችግሮች ለማስተካከል ብለን በመድረክ፣ በፅሁፍ፣ በክስ መልክ ደረጃውን ጠብቆ ህገ ደንብን መሰረት በማድረግ ለ9 ወራት ጠይቀናል። ሌሎች በራሳቸው ይገልፁት ይሆናል። እኔ የሄድኩበት መንገድ ልግለፅ ፤ከ2003 እስከ 2005 በማ/ኮሚቴና ስራ አስፈፃሚ በፓርቲያችን መጥፎ ሁኔታ እንዳለ አንድ በአንድ ዘርዝሬ አቅርቤ ነበር። በተለይ ደግሞ በ2005 በአረና ውስጥ ስል አንድነትና ውህደት የላላ አቋም እንዳለ፤ አባታዊነትና አምባገነንነት ባህርያት እንዳለ፤ ከማ/ኮሚቴ እስከ ታች የተዘረጋ ቡድናዊነት ወዘተ. እንዳለ በአጠቃላይ ከላይ የገለፅኳቸው የፓርቲው ችግር እንዲስተካከሉ አንስቼ ነበር፤ በ3ኛ ጉባኤም በመድረክ አንስቼዋለሁ፤ ከጉባኤ በኋላም ከጥቅምት ወር 2006 ጀምሮ በማ/ኮሚቴ በተለይ በሊቀመንበሩ ስለ ሃገራዊ አንድነትና ውህደት የሚታዩ ችግሮች፤ ቡድናዊነት በማስፋፋት አባላቱ እንዲፈርሱ ሚደረገው መጥፎ ስራ፤ ከህወሓት ካድሬዎችና አመራሮች የጠበቀ ግንኙነት መኖር እስከ በህብረት ሲሚንቶ መንገድ ወዘተ. ብየ አጀንዳ በመያዝ መቀሌ ካሉ 5 ስራ አስፈፃሚዎች እንዲያወያዩን ጠይቄ ብርሃኑ አፍኖ ለ2 ወር ቆየ፤ እኔም ተስፋ ሳልቆርጥ ብርሃኑ ግብረገብነት የጎደለውና ህገ-ደንብን በመጣስ ህገ ወጥ ስራ እየሰራ ነው ይታይልኝ በማለት ለጠቅላላ ማ/ኮሚቴ አመለከትኩ፡፡ ለ32 ቀናት ታፈነ፡፡ ቀጥሎ 13 አጀንዳዎች የያዘ አቀረብኩ፡፡ አልተቀበሉትም፡፡ ቀጥሎ ሊቀመንበሩ ማኸል ያደረገ 4 ጊዜ ለቁ/ኮሚሽን ክስ አቀረብኩ፡፡ ቁጥጥር ኮሚሽንም ለ2 ወራት ዘጋው፡፡ በቃ አፈናው በረታ፡፡ መጨረሻ አስቸኳይ ጉባኤ ጠርቼ አሁንም ተዘጋሁ፡፡ መጨረሻ በአረና ስራ አስፈፃሚ የታፈነው ጥያቄ 15 ነጥቦች የያዘ 5 ገፅ ሰነድ ለአረና አባላትና ደጋፊዎች ብቻ አሰራጨሁ፡፡ ሁሉም በፅሁፍ ያቀረብኳቸው ጥያቄዎች የአረና ፅ/ቤት ፈርሞ ተቀብሎታል፡፡ በመዝገብ ቤቱ ይገኛል።
ለ9 ወራት ያመለከትኩት ጥያቄዎች ከአረና አመራር ውስጥ በግልም ይሁን በቡድን ያነጋገረኝ ሰው የለም፡፡ አንፃሩ ብርሃኑ በርሄና ጥቂት አጃቢዎቹ በጥላቻ አይን እያዩ በሃሜት ስሜን እያጠፉ ቆይተዋል። በእኔ እምነት አንድ ዲሞክራሲያዊ መሪ ይቅርና ከአባላቱ ለሚነሱ ጥያቄዎች ከማንም ሰው ለሚነሳ ጥያቄ በማዳመጥ መፍትሄ የመስጠት ግዴታ አለበት፡፡ ከዚያ አልፎ በቅርብ ርቀትና በርቀት እየተከታተለ ምን አይነት ሁኔታ እንዳለ በመከታተልና ኢንፎርሜሽን በማሰባሰብ ጥያቄዎቹ እሱ ላይ ከመድረሳቸው በፊት መፍትሄ ማስቀመጥ ይገባ ነበር፡፡ ብርሃኑ በርሄ፣ 3ቱ ጓደኞቹና አጃቢዎቹ ግን ለዚህ አይነት መልካም አመራር አልታደሉም፡፡ ይኸ ደግሞ ሆን ተብሎ አረናን ለማዳከምና እነሱን የሚፈታተን መሪ እንዳይወጣ አባላቱን በማመናመን እነሱ ደግሞ በዚህ ምሽግ እድሜ ልካቸው እንዲኖሩበት እኩይ ተግባር ነው። 

የተከበራችሁ ወገኖች የአረና ማ/ኮሚቴ ለ9 ወራት ሙሉ ሲያፍነኝ እኔ ግን ምንም ቂም ሳልይዝ አንድ ቀን ይፈታል ብየ ተስፋ በማድረግ ለአፋኙና አምባገነኑ የህወሓት ኢህአደግ ስርአት ለማጋለጥ ከአረና ማ/ኮሚቴ ሆነ ስ/አስፈፃሚ በላይ ግምባር ቀደም በመሆን በህወሓት ባንዳዎች እየተደበደብኩ በጎዳና ደሜን እየነዘረ እየታሰርኩ እልህ አስጨራሽ ትግል ሳደርግ ቆይቻለሁ፡፡ እነ ብርሃኑና አጃቢዎቹ ለመናገር የሚፈሩት እኔ፣ አብርሃ ደስታና መ/ር ታደሰ ቢተውልኝ ነበር፡፡ ህዝቡን ማሳመን የቻልነው ህዝቡም የነ ብርሃኑ ተወላዋይነትና የኛ ጥንካሬ ነግሮናል፡፡ በሌላ በኩል በሃገር ውስጥና በውጭ ሚዲያዎች አምባገነኑ ስርአት ስናጋልጥ ብርሃኑ በርሄ ሚዲያዎች መረጃ ፈልገው እንደ ሊቀመንበር ሲጠየቅ እምቢተኝነቱን ነው ያሳየው፡፡ አስፈላጊ ከሆነ ወደፊት እገልፀዋለሁ፡፡ ብርሃኑ በርሄ ግን አፉን ሞልቶ በአረና አፈና የለም ማለቱ ምን ያህል ሞራል አልባ መሆኑ ያሳያል። ብርሃኑ በርሄ እስካሁን ከአባይ ወልዱ የማይተናነስ አረናን እያፈነ ይገኛል፡፡ ጭራሹም ወደ ህወሓት ለመቀላቀል በበር መዝግያ ከፍቶ ለመግባት በፍጥነት የሚያጋልጠው ስለሆነ በምርጫ አማካኝነት በጓዳ በመግባት በፓርላማ የህወሓት አፈና ሟሟያ እንዲሆን አዘጋጅቶ የተቀመጠ ነው የሚመስለው።
ይህ ካልኩ በኋላ እኔና ሌሎች ጥያቄ ያነሱ ወገኖች ባለፈው ሀምሌ 19ና 20/2006 ዓ.ም የማ/ኮሚቴ መደበኛ ስብሰባ ጥያቄያችን መልስ ያገኛል ብለን ነበር፡፡ በተለይ አቶ ገብሩ አስራት ከአሜሪካ በሮ መምጣቱ ችግሩ በሰላማዊና በበሰለ መንገድ ይፈተዋል ብለን ነበር፡፡ ውጤቱ ግን የባሰ አፍራሽና የገብሩ ማንነት በማያጠራጥር ያጋለጠው ሁኖ ነው የተገኘው፡፡ እንደውም አቶ ገብሩና ጓዶቹ በጓሮ ወደ ህወሓት ለመግባት ፈልገው ይሆናል? የሚል ሃሜት እየተናፈሰ ሰንብተዋል፡፡ ምክንያቱም ጠንካራ አባላት ማባረር ለህወሓት እንደ መጠናከር ለአረና እንደመፍረስ ማለት ነው የሚሉ ወገኖች ብዙ ናቸው። 

ብርሃኑ በርሄ፡- ‹‹በፓርቲ የምንወስደው ቅጣት ደረጃ በደረጃ ነው›› ይላል፡፡ በኔ ላይ የተወሰደ እርምጃ 1ኛ የከሰሰኝ ማነው? 2ኛ ያ ቁጥጥር ኮሚሽንስ አይቶታል ወይ? 3ኛ ያጠፋሁት ጥፋትስ አይነገረኝምን? 4ኛ የተጣለብኝ ውሳኔስ በወሰነልኝ ኣካል በስርአት በደብዳቤ ሊሰጠኝ አይገባምን?
ብርሃኑ በርሄ፡- ‹‹አስገደ 2005 ከባድ የስነ ምግባር ጉድለት በማሳየቱ በቁጥጥር ኮሚሽን ማስጠንቀቅያ ተሰጥቶት ነበር፤ አሁንም ሊያሻሻል ስላልቻለ ተባረዋል›› ይላል፡፡ ለመሆኑ የተፈፀመው የስነ ምግባር ጉድለት ምንድ ነው? የተሰጠኝ ማስጠንቀቅያስ ለማ/ኮሚቴ ወይ በጠቅላላ 3ኛ ጉባኤ መገለፅ አልነበረበትምን? ለመሆኑ ቁጥጥር ኮሚሽን ለአንድ ስራ አስፈፃሚ ማስጠንቀቅያ የመስጠት ወይ የመቅጣት ስልጣንስ አለዉን? ለመሆኑ አሁን ያባረሩኝ የመቀሌ ዞን መሰረታዊ ድርጅት የሚባሉ አዛውንትስ እነማን ናቸው? ማነው ጠፍጥፎ ያቋቋማቸው? መቀሌ’ኮ አባል የሚባል የለም፡፡ ስለዚህ የብርሃኑ ማጭበርበር ካልሆነ በስተቀር እኔ በአረና በነበርኩበት 6 አመታት በሁሉም ዞኖች ያሉ አባሎቻችን አንድም ቀን ሂስ አድርጎልኝ አያውቅም። በአንፃሩ ብርሃኑ ያባረራቸውና ያበሳጫቸው አባሎቻችን ለማግባባትና ለማበረታታት ተጠምጄ ነው የኖርኩት፡፡›› በነገራችን ላይ የአረና ስራ አስፈፃሚ እንዳባረረኝ በአዲስ አድማስ ጋዜጣ ተናግረዋል፤ በሌላ በኩል ደግሞ ይግባኝ ማለት ይችላል ብለዋል፤ በአንድ መሰረታዊ ድርጅት የተወሰነ ስህተት በስራ አስፈፃሚና ማ/ኮሚቴ ሊቀየር ይችላል፡፡ ነገር ግን ይግባኝ ከማለቴ በፊት ያየመጨረሻ ብይን ይሰጣል የሚባል የፓርቲው አካል በራሱ አባርሮኛል፡፡ በመሰረታዊ ድርጅት ይሁን በስራ አስፈፃሚ የተወሰነው የውሳኔ ደብዳቤ 4 ጊዜ ብለምናቸውም ሊሰጡኝ አልቻሉም፡፡ በአንዳንድ የፓርቲው ማ/ኮሚቴ አባላት ለምሳሌ እንደ ሃፍታይ ወልደሩፋኤል እንዲያሰጡኝ ብለምናቸውም ሊሰጡኝ አልቻሉም፡፡ ታዲያ በየትኛው የስንብት ደብዳቤ ለየትኛው አካል ነው ይግባኝ የምለው? የብርሃኑ የውሸት ሰደድ አድርጌ ነው የምመለከተው።
ብርሃኑ በርሄ: ‹‹በአረና የውስጥ ችግር የለም፡፡ ፓርቲው በፕሮግራም በእስትራተጂ አልተለያየም፡፡ እንደ አንድ አካል ሁነን ተስማምተን እንሰራለን፡፡ በአንድ ሁነን ሁሉም የፓርቲ እቅዶችን እያወጣን እንሰራለን፡፡ አንድ ሁለት ሰዎች ከራሳቸው ምክንያት ተነሳስተው ስማችን እያጠፉን ያሉት ውሸት ነው›› ይላል፡፡ በአረና እስካሁን የተደረጉ ስብሰባዎች፣ የአባላት ስልጠና ተብየዎች፣ የማ/ኮሚቴ ስብሰባዎች፤ የስራ አስፈፃሚ ስብሰባዎችና ጉባኤዎች በህገ ደንቡ መሰረት የሚመለከታቸው አካለት አጀንዳ ይዘው ተወያይቶበትና ተግባብተው ሳይሆን ብርሃኑና 3ት ስላሴዎች በፈለጉትና ባቀዱት ብቻ እየተካሄዱ ቆይተዋል። ህገ ደንቡ ግን የማ/ኮሚቴ ስብሰባ ሲደረግ ስራ አስፈፃሚ አጀንዳ አዘጋጅቶ ከስብሰባ በፊት ለኩሉም ማ/ኮሚቴ ከ7 ቀናት በፊት ያሰራጫል።

እስካሁን ሲሰራ የነበረ ግን የሚቀርቡ አጀንዳዎች በብጣሽ ወረቀት በሊቀመናብርቱ ይቀርባል፡፡ ይህ ተግባር በ2004፣ በ2005 በ3ኛ ጉባኤ ህገ-ደንብ ተጥሰዋል እየተባለ በተደጋጋሚ ሲነሳ ንሯል፡፡ አቶ ገብሩ አስራት ግን በጣም ያበሳጨው ነበር፡፡ በአረና ትግራይ እስካሁን ድርጅታዊ አሰራር ተግባራዊ ተደርጎ አያውቅም፡፡ ኮሚቴአዊ አሰራር የሚያስፈልገው በኮሚቴ ተወስኖ አያውቅም፡፡ አሁንማ እቺ ፓርቲ የብርሃኑ በርሄ፣ 3ት ስላሴዎችና ጥቂት ባንዳዎች የግል ድርጅት ነው ቢባል ይቀላል። ሌላ ውህደትን በተመለከተ የህወሓት ሌጋሲ በመከተል አረና ክልላዊ ፓርቲ መሆኑ ቀርቶ ራሱ ሃገራዊ አውራ ፓርቲ ሊሆን ነው፡፡ ይህ ካልሆነ ደግሞ የትምክህተኛ አማራ ፓርቲዎች መሰባሰብ ሊውጠን ነው የሚል ጠባብ አስተሳሰብ ራሱ ትልቅ የስተራተጂና የፕሮግራም ልዩነት ነው። በነገራችን ላይ አረና በቃል ካልሆነ በስተቀር የቅርብና የሩቅ እስትራተጂ በሰነድ የተነደፈ የለም። ሌላ በውስጥ መከፋፈል የለም የሚለው እነ ሰለሞን ገ/አረጋዊ፣ ብርሃኑ መለሰ (ብርሃኑ ሞርታር)፣ አስራት አብርሃም፣ ጉዕሽ ገ/ፃዲቅ፣ ስልጣኑ ሕሸ፣ ይልማ ይኩኖ ወዘተ. ፓርቲው ውስጥ ባለው ችግር አይደለምን የወጡት? አሁን ደግሞ ታደሰ ቢተውልኝ፣ ገብሩ ሳሙኤል፣ ሽሻይ አዘናውና እኔ ራሴ ያነሳነው መሰረታዊ ጥያቄዎች ማለት የህገ-ደንብ አለማክበር፣ የተጠያቂነትና ኮሚቴአዊ አሰራር ግድፈት ስንቃወም አንድነትን ያመላክታል። አረና ትግራይ በመጋቢት 20/2000 የትግላችን የሩቅ አላማ በሃገራችን ከሚገኙ ማናቸውም ሃገራዊና ክልላዊ ዲሞክራሲያዊ ሃይሎች ከቅንጅት እስከ ውህደት በመጓዝ አንድነቷና ሉአላዊነቷ የተረጋገጠ ዲሞክራሲያዊት ኢትዮፕያን ለመመስረት ነው ብለን በሃሳብ ከተስማማን በኋላ በዛ መሰረት ተጉዘን እስከ ግንባር ተጉዘናል፡፡

ውህደትን በተመለከተ ግን ያ ሃገርን ያበላሸ የህወሓት ጠባብ አስተሳሰብ አገረሸባቸውና ብርሃኑ በርሄና 3ት ስላሴዎች የአንድነትና መኢአድ መሰባሰብ አማራን አጠናክረው የበላይነታቸው ለማረጋገጥ ስለሆነ ከአንድነትና ሌሎች የትምክህት ሃይሎች አናብርም ብለው የህወሓት የ1968 አቋም ይዘው ቁጭ ማለታቸው የእስትራተጂ ስህተት ከመሆኑ አልፎ ሃገርን የማስገንጠል አቅጣጫ የሚከተሉ ይመስላሉ። የአንድ ብሄር ፓርቲ የኢትዮጵያ አውራ ፓርቲ እንሆናለን ካላችሁ ከህወሓት በምን ትለያላችሁ? ለምን ፊትለፊት የህወሓት በር ከፍታችሁ ህወሓትን አትቀላቀሉም? ለምን በስመ ተቃውሞ በጓዳ መግባት አስፈለገ? ስለሆነ አሁንም ብርሃኑ በርሄ አታጭበርብር! ጠበቃ ስለሆንክ አልሸነፍም ብለህ እየተሟገትክ ከሆነም አሁን አይደለህም የተሸነፍከው ከተሸነፍክና ከተነቃብህ ቆይቷል። 

ፕሮግራማችን የግለሰው መብት የሚያስቀድም ነው፡፡ በነብርሃኑ ግን ጥያቄ ላነሳ ግለሰብ ይቅር በማ/ኮሚቴ በቡድንና በተናጠል የሚቀርቡ ጥያቄዎች ተቀባይነት የላቸውም፡፡ በአንፃሩ የአረና ፈላጭ ቆራጭነት የነገሰበት ሁኔታ ነው ያለው፤ ግለሰዎች ነፃ ሁነው ሃሳባቸውን መግለፅ አልቻሉም። 

ብርሃኑ በርሄ ‹‹የነዚህ ሰዎች አቀራረብ እነሱ ራሳቸው ለነበራቸው ሃላፊነት የሚያበቃ እውቀትም ሆነ ስነ ምግባር እንደሌላቸው ለአንባቢ ያስረገጡበት ሁኖ ነው የተሰማኝ›› ይላል። የአንድ ሰው እውቀት መመዘኛ የህወሓት ጠባብ አስተሳሰብ በማራመድ ሃገርን ለመገነጣጠል ማቀድ፣ ከህገ-ደንብ በላይ ሁነህ መገኘት፣ አባላትን በማባረር፣ ስርአትና ግብረገብ አልቦ ወዘተ. ከሆነ ብርሃኑ እውነት አዋቂ ነህ፡፡ አለበለዚያ የአንድ መሪ እውቀት ዲሞክራሲያውነት፣ ተጠያቂነት፣ ግልፅነት፣ የሰዎችን ሃሳብ ማዳመጥና በብቃት መመለስ፣ በሀገ-ደንብ መገዛት፣ መሪዎችን በማፍራት የድርጅቱን ራኢይ ብሩህ የሚያደርግ በአጠቃላይ ለህዝብና ሃገር ጥቅም መቆምና መስዋእት መሆን ከሆነ ብርሃኑ መሃይም ነው ማለት ይቀላል። እኛ’ኮ ህገ ደንባችን ይከበር፣ ለህዝብና ሀገር ጥቅምና ክብር መስዋእት እንሁን፣ ከጠባብ አስተሳሰብ ወጥተን ለተዋሃደች ኢትዮጵያ እንቁም፣ ለሆዳችን መገዛት ትተን የገባነው ቃል እንፈፅም፡፡ በአጠቃላይ ህገ ደንባችን ፕሮግራማችንና አላማችን ተንዷል ነው እያልን ያለነው። ይኸ አለማወቅና ሃላፊነትን አለመወጣት ከሆነ አንባቢ ይፍረደን፡፡ ብርሃኑ ግን ካሁን በፊትም አህያ ግብሯን አይቶ ቀንድ ከለከላት ብሎ በኢትዮ ምህዳር ጋዜጣ ከአህያ ጋር አመሳስሎናል፡፡ የአህያ አስተሳሰብ የታደለ ማን እንደሆነ ፍርዱ ለአንባቢ ትቼዋለሁ። 

ብርሃኑ በርሄ፡- ‹‹ … ሽሬን በጎጠኝነት ካነሱ ሽሬ የብቻቸው እንዳልሆነች መከራከሩ ብዙ ባያስፈልግም የሽሬ አረና አባላት እነዚህ አሁን በጎጠኝነት ተባረርን አሉ ያልከኝ ወደ ሽሬ እንዳትልኩልን እንዳሉ በማ/ኮሚቴው ስብሰባ ከፈጠሩት ችግር ተያይዞ ተነግሮአቸዋል….. አቶ አስገደ የጎጥ ፕሮጀክት ሽሬን ተንተርሶ በጎጥ መክሰስ መጀመራቸው የህወሓትን አርማ ደግመው ማንሳታቸው ካልሆነ አንዳች እውነታም ሆነ ምክንያት የለውም›› ይላል። መጀመርያ ከላይ የዋሸኸው በሽሬ ያሉ አባላት እነዚህ ሰዎች እንዳትልኩልን ብለውናል የምትለው በነሱ ፊት አትደግመውም፡፡ እጅጉን ሰነፍና ውሸታም ተከራካሪ ስለሆንክ፡፡ ሁለተኛ እኔ አስገደ በጎጠኝነት አልታማም፡፡ አረና ከተመሰረተ በሁሉም የትግራይ ዞኖችና ወረዳዎች እስከ ቀበሌ ድረስ ተንቀሳቅሼ ለዚህ ፓርቲ ብዙ አባልና ደጋፊ አፍርቼአለሁ፡፡ በትግራይ ያለው ሙሁሩ፣ ገበሬው፣ ነጋዴው ወዘተ. ያውቀኛል፡፡ አንተ ደግሞ በአንፃሩ መለያህ ጎጠኛነትህ ነው፡፡ እጅጉን የወረድክና ውሸታም መሆንህ ደግሞ ሽሻይ አዘናው የእህቱ ልጅ ማለትህ ሀቀኛ እንቅስቃሴ ወደ ዘረኝነት አቅጣጫ ለማስቀየር መሞከርህ ነው፡፡ የራያ ትውልድ መኖሬንም ብታውቅ ኑሮ ገብሩ ራያንም የወንድሙ ልጅ ትለው ነበር፡፡ ይህ ተግባርህ ደግሞ የጌታህ ህወሓት ጠባብ አስተሳሰብና የጎጥ አርማ እያነሳህ ያለኸው አንተ ራስህ ነህ፤ በተግባርም ለአረና ጎድትሃታል፡፡ ባዶዋን አስቀርሃታል፡፡ ከህወሓት እጅና ጓንት ሁነህ እየሰራህ ያለኸው አንተ ነህ፡፡ እስኪ አንድ ነገር ልጠይቅህ፡፡ እንኳን የአረና አባል ደጋፊ ነው ተብሎ የተጠረጠረ እንኳን መሳርያው እየተነጠቀ ባለበት ሁኔታ አንተ በምን መስፈርት ነው በምልሻነት ነፍጥ የታጠቅከው? እኔና ሌሎች ንፁሃን አባላትማ እንኳን መሳርያ ሊፈቀድልን ልጆቻችንና ዘርመንዘራችን የ3ኛ ዜጋ መብትም የለንም። 

ብርሃኑ በርሄ፡- ‹‹አብርሃ ደስታ የአረና የህዝብ ግንኙነት ኮሚቴ አባል ስለነበረ ሃላፊነቱ በአግባቡ ተወጥተዋል ብቻ ሳይሆን ብቁ የፖለቲካ መሪ ሁኖ ሊወጣ ተስፋ የሚጣልበት መሆኑ ደጋግሜ ስለው የነበረ ነው›› ይላል። አብርሃ ደስታ ወደ አረና ከመቀላቀሉ በፊት 2 አመት አስቀድሞ ከኔ ጋር ነበር የተገናኘው፡፡ ከአብርሃ ደስታ በሳምንት ቢያንስ 2 ጊዜ እንገናኝ ነበር፡፡ በኋላ ግን በየቀኑ እስከ ሁለት ጊዜ እንገናኝ ነበር ስለ አብርሃ ደስታ ብዙ ጊዜ እነግርህ ነበር፡፡ ደስ ግን አይልህም ነበር፡፡ አባል ይሁን ፎርም ይሙላ ስልህ ይቆይ እናጥናው ነው ያልከኝ፡፡ ሰውየው በማህበራዊ ድረ-ገፅ እየታወቀ ሲመጣ አንተ ደስ አይልህም ነበር፡፡ ነገር ግን በኔ ተፅእኖ ወደ ፓርቲው ተቀላቀለ፡፡ እነ ስልጣኑም በጥሩ ሁኔታ ስለያዙት በአጭር ጊዜ ውስጥ በአባላት ታዋቂ ሆነ፤ በ3ኛ ጉባኤም ለፕረዚዴም ሲመረጥ አልተደሰትክም፡፡ በኋላም ለአረና ህዝብ ግኑኝነት ሲጠቆምም አቶ ገብሩ አስራት በፀረ-ዲሞክራሲ ያለጥቆማና ድምፅ አምዶም መሆን አለበት ብሎ ያለድምፅ አፀደቀለት፤ ለህዝብ ግንኙነት ምክትልም አብርሃ የተጠቆመ እያለ ባንተ ጥቆማ ፍፁም ግሩም ሆነ፤ ስለሆነ አብርሃ ደስታ ጥሩ መሪ እንዲሆን ፍላጎት አልነበራችሁም፡፡

አብርሃ ደስታ በማህበራዊ ድህረ ገፆችና ሚዲያዎች በሚያደርገው እንቅስቃሴ ትእግስት አድርግ እያልክ ተፅእኖ ታደርግለት ነበር፡፡ እሱ ግን እኔ የግለሰብ ነፃነቴ ካላከበርኩ እንዴት ነው የህዝብ ነፃነት ማከብረው ብሎ ተቃውሞሃል፤ አቶ ገብሩ አስራትም የአብርሃ ደስታ እንቅስቃሴ ከፓርቲያችን አቋም ይሄዳል ወይ ብሎ ሲጠይቅ አሁንም ተቃውሞታል፤ እኔጋ በነበረው ግንኙነትም እንደ ቡድን ትቆጥረው ነበር እሱ ግን አልተቀበለህም፤ በአጠቃላይ በአብርሃ ደስታ ያለህ አመለካከት የቅናት እንጂ የፍቅር አይደለም፡፡ ለዚሁ እንደ ማስረጃነት አብርሃ ደስታ በጠራራ ፀሃይ ሲታፈን እኛ በየፖሊስ ጣቢያ ስናፈላልግ አንተ ግን በጥብቅና ቢሮህ ሁነህ ራፖልህ ነበር የምትሰራውና ገንዘብ የምትለቅመው፤ ደብዳቤ ፅፈን ፈርምልን ስንልህም ደስተኛ አልነበርክም፡፡
አብርሃ ደስታ ሲታሰር መግለጫ ከመስጠት ተቆጥበሃል፤ እኔ በኢሳትና ሌሎች ሚዲያዎች ስለ አብርሃ ስፅፍ አንተና አምዶም በውጭ ሚዲያ ተጠይቃችሁ ፍቃደኞች አልሆናችሁም፡፡ ስለ አብርሃ መታሰርም ለአባላት አልተናገራችሁም፤ ብዙ አባላት ጠበቃ እናቁምለት ብለው ሲጠይቁም ይቅርና ጠበቃ ለማቆም ሂዳችሁ’ኳን ለማየት አልሞከራችሁም፡፡ መጨረሻም ጠበቃ ልታቁምለት የተገደዳችሁበት ምክንያት አንድ ወገን በራሱ ሊጣበቅለት ሲወስን እንዳትታሙ እንከፍላለን ብላችሁት፡፡ ታዲያ የቱ ጋ ነው አድናቆቱ? የት ነው ፍቅሩ? መልሱ ላንተ። 

ብርሃኑ በርሄ፡- ‹‹በአብርሃ ደስታ አሳብበው የራሳቸው ፍላጎት ማስተንፈሻ ለማድረግ የሚፈልጉ ሰዎች መኖራቸው እናውቃለን ግን ያላወቁት ሁነው ነው’ጂ አብርሃ ደስታ ባለፉት 9 ወራት ስራ አስፈጻሚ ሁኖ የአረና ባህሪና አመራር ያውቀዋል፡፡›› ይላል። በመሰረቱ በአብርሃ ደስታ ምናስተነፍሰው ነገር የለም፤ ያንተ ጨካኝነትና ከዳተኝነት አብጠርጥረን እናውቃለን፤ አብርሃ ደስታ በናንተ እጅጉን አዝኖ እንደ ነበረ ታውቃለህ፤ የህወሓት ካድሬዎች የሚያስቆጣ ነገር እንዳትናገሩ ስትለው አልነበርክም፤ አብርሃ በደንብ ሚያውቃችሁ በፀረ-ዲሞክራሲ አስተሳሰባችሁ፤ አባታዊነታችሁ፤ በአምባገነናዊነታችሁና ቡድናዊነታችሁ ነው፤ በናንተ በጣም ተስፋ ቆርጦ እንደነበር ይነግረኝ ነበር፤ እንደውም አስገደና አብርሃ ደስታ እኛን ከድተው አንድነትን የሚቀላቀሉ በግምባር ቀደምትነት እንደምንጠቀስ አጃቢዎችህ ያሙን ነበር፤ አሁን በውጭም በውስጥም ደጋፊ ስለበዛ ቀንተህ ነው። አብርሃ ደስታ’ኮ ባሳየው ጠንካራ ተቃውሞ አሸባሪ ተብሎ ነው የታሰረው፤ አንተ ግን አሸባሪ እንዳትባል ከህወሓት ተለማምጠህ ትኖራለህ። 

ብርሃኑ በርሄ፡- ‹‹ክላሽ የለኝም ሽጉጥ ግን አለኝ ባለ ፍቃድ ነው፤ ሽጉጡ በትጥቅ ጊዜ እኔጋ የነበረ ነው፤ በትጥቅ ትግል ታጋይ በመሆን ትጥቁ የያዙ ፓርቲው ጋር ቢቀጥሉም ባይቀጥሉም አልተነጠቁም፤ ሊነጠቁም አይገባም፤ አቶ አስገደ ገ/ስላሴም ሽጉጥና ክላሽ ነበረው አሳበው ችግር እንዳይፈጥሩብኝ ትጥቄን አስረክቤያለሁ ብሎ በ2000 ነግሮኛል…››
አሁንም ብርሃኑ እየሸፈጥክ ነው፤ በኢትዮጵያ የፓርቲዎች ማቋቋምያ አዋጅ ማንም ፓርቲ ነፍጥና ሰውን የሚጎዳ መሳርያ አይታጠቅም፤ መንግስት ካቋቋማቸው ፖሊስ፣ መከላከያ ፣ ደህንነት ብቻ ይታጠቃሉ፤ የህወሓት አባልም ከነዛ የመንግስት የፀጥታ ሃይሎች ውጪ የሆኑ ትጥቃቸው ያራግፋሉ ይላል፤ በዚህ መሰረት ሁሉም ተቃዋሚ ሃይሎች ማንም ነፍጥ የታጠቀ የለም፤ ህወሓት እንደ ሆነ ራሱ ዳኛ ልጁ ቀመኛ ዳኛ የለውምና በትግራይ ክልል ብቻ በምልሻ ስም ካድሬ አመራሮች በአንድ ቀበሌ ከ72-90 ታጣቂዎች አሉ፡፡ እነዛ ሁሉ ለተቃዋሚ ፓርቲዎች ስጋት ናቸው፡፡ ይህ የሆነበት ህወሓት ፀረ-ህገ መንግስት ስለ ሆነ ብቻ ነው። ታዲያ ብርሃኑ የፓርቲ ሊቀመንበር ሁኖ ነፍጥ መታጠቁ የህወሓት ልጅ አይደለምን? ምልሻ ታጋይ የነበሩ አሁን የአረና አባላት የሆኑ ነፍጣቸው ተቀምተው በሁሉም መልኩ መብታቸው ተነጥቀው እየተሰቃዩ ነው፡፡ ይቅርና አባል ዘመድ አዝማድ እየተቆጠረ ተፍጓቸዋል። ታዲያ ብርሃኑ እንዴት አድርገህ ታታልለናለህ? እኔ በተደጋጋሚ ትጥቃችን እናስረክብ፤ ለራሳችን ነፃ አድርገን ለህወሓት ሲቪል ታጣቂዎች እንዲያስረክቡ እናድርግ ብየው እምቢ ብሎኛል።

አሁን ብርሃኑ ፍቃድ አለኝ ብሎናል፤ ፍቃድ የሚሰጠው በደህንነት ወይ በፀጥታና ፍትህ ነው። በመሆኑ ብርሃኑ ደህንነት ወይ ሚሊሻ ካልሆነ ፍፁም አይፈቀድለትም፤ ስለዚህ ብርሃኑ ደህንነት ወይ ሚሊሻ መሆኑ እያረጋገጠልን ነው። ደህንነትና ሚሊሻ ደግሞ የህወሓት ካድሬዎች ናቸው። ስለዚህ ብርሃኑ በርሄ የህወሓት አባል ነው፤ በኛ ላይ የተወሰደ እርምጃም አረናን ለማዳከም ተብሎ ነው።
ማሳሰቢያ:
1.የአረና አባላትና ደጋፊዎች በአረና ውስጥ ያለ ልዩነት በኔና በብርሃኑ የግል ንትርክ አድርገው የሚመለከቱ አባላት አሉ፤ ይኸ ፍፁም ስህተት ነው፤ የግል ቂምም የለኝም፤ ልዩነታችን በብርሃኑና በ3ት ስላሴዎችና በኛ ያለው ከላይ በተዘረዘሩ ችግሮች ምክንያት ነው፤ እነሱ ተሸፍነው ለመሄድ ሲሞክሩ እኛ ችግሩ መታገላችን ብቻ ነው ልዩነታችን፤

2.ውህደትን በተመለከተ እኛ ለመላው የኢትዮጵያ በእኩል የሚያስተናግድ፤ ህዝቡን ከዘር ፖለቲካ አውጥቶ በህዝቦች ጠንካራ መተማመን እንዲሰፍን፤ ክብሯና ሉአላዊነቷ የተረጋገጠች ኢትዮጵያን ለመገንባት ከማንኛውም ኢትዮፕያዊ ያለ ጥርጥርና ስጋት መወሃሃድ ስንፈልግ እነሱ ደግሞ ልክ የህወሓት አቋም እያራመዱ ስለሆነ ነው፤ በተለይ ብርሃኑ አባላት ሰብስቦ ከነ አንድነት ለውህደት ብየ አልደራደርም፤ አንድነትና ሌሎች ፓርቲዎች በመወሃሃድ የትግራይን ስነ ልቦናዊ ፍላጎት አያከብሩም ወዘተ. በማለቱ ነው፤

3. በዲያስፖራ የአረና ድጋፍ ሰጪ ኮሚቴ አመራርና አባላት እኛ ያነሳነው ጥያቄ ረጋ ብለው ምን እየተባለ እንደሆነ አስበውና አጣርተው አቋም እንደመውሰድ የነ ብርሃኑ የአንድ ወገን ሃሳብ ብቻ በማዳመጥ ጥያቄያችሁ በውስጥ እንደ መፍታት የትምክህተኛ አማራ መሳቂያ አደረጋችሁን ብላችሁ ፅሁፍን ማሰራጨታችሁ ከህወሓት ጠባብ አስተሳሰብ እጅጉን የወረደ ነበር፡፡ በእርግጥ ፅሁፉ የሁሉም ዲያስፖራ ደጋፊያችን እንደማይወክልና የጥቂት የነብርሃኑ አጃቢዎች አስተሳሰብ ብቻ ብለን ነው የምናምነው። እኛ ግን ከዚህ ሁሉ ጠባብ አስተሳሰብ ነፃ ነን።

4. በኔ እምነት ለህወሓት ተሸክመን መጥተን ሃገር አጠፋን፤ እንደገና ሁለተኛ ህወሓት የሚሸከም ትክሻ የለንም። አሁንም እኔ ለአምባገነኑ የህወሓት ስርአት በሰላማዊ መንገድ ከመታገል ወደኋላ አልልም፤ ለኢትዮጵያ አንድነት፤ ሉአላዊነት በአጠቃላይ የኢትጵያ ችግር ለመፍታት ቆርጦ ከተነሳ ሃይል በመሰለፍ ትግሌን እቀጥላለሁ፤ ለህወሓትና ለተበላሸው የአረና አመራር እኩል እታገለዋለሁ።
ድል ለኢትዮጵያ ህዝብ‼

አንጀሊና ጆሊ ኢትዮጵያ ውስጥ የሰራችው ”ድፍረት” ፊልም በፖሊሶች ታገደ (አቤ ቶኮቻው)

$
0
0

አቤ ቶኮቻው

አንጀሊና ጆሊ ኢትዮጵያ ውስጥ የሰራችው ”ድፍረት” ፊልም በፖሊሶች ድፈረት በርካታ ”ትላልቅ” እንግዶች በተገኙበት ሊመረቅ ሲል ታገደ፤ አርቲስቶች አዝነዋል እኛም የጥንቸሏን ተረት አስታውሰናል…

409864572-12ሜሮን ጌትነት በመሪ ተዋናይነት ሰርታበታለች የተባለው ይህ ፊልም የታገደው በፖሊሶች ቀጭን ትዛዝ ነው። በርካታ አርቲስቶች የዚህ አይነት ነገር ሲያጋጥማቸው ለመጀመሪያ ግዜ መሆኑን ተናግረዋል። እኛ ግን የነጻ ጋዜጠኞች ማህበር ስብሰባ ፖሊስ በትኑ ሲል ሰምተን እናውቃልን እና፣ የተቃዋሚ ፓርቲዎችን ሰብሰባዎች ከተሰበሰቡ በኋላ ብዙ ጊዜ አምቦውሃው መንግስታችን ሲበትነው አየተናልና፣ የባለራዕይ ወጣቶችን ሰላማዊ ስብሰባ በተደጋጋሚ ያለምንም ሀጋዊ ከለላ ሲያገደው አየተናልና… የዳዊት ጸጋዬ ቲያትር ማስመረቂያ አጥቶ ከሰማያዊ ፓርቲዎች ጋር ቦታ ፍለጋ ሲነከራተት መሰንበቱን እናውቃለነና ኧረ ስንቱ…

(በነገራችን ላይ ዘ ዲክታተር የተባለው አስቂኝ ፊልም እንኳ፤ ባንድ ወቅት ርሳቸው ሬሳ ከመሆናቸው በፊት…(ውይ እኔ ደግሞ አንዳንዴ አበዛዋለሁ አቶ መለስ ”ከመሰዋታቸው” በፊት ማለቴ ነው… እና ያኔ ታግዶ ነበር።) ይሄንን ሁሉ ያልሰሙ አርቲስቶች ዛሬ ተደነቁ እንጂ መንግስታችን ማገድ ብርቁ አይደለም።

የጥንቸሏ ተረት ምን መሰላችሁ…

ዝሆን እና ጥንቸል ሲኒማ ቤት ተገናኙ አሉ፤ ከዛ ዝሆን ሆዬ ከጥንቸል ፊት ሄዱ ቁጭ ብሎ ከለላት አይገልጸውም…(ከፊልም ቤት አስወጣት ብንል ይሻላል…ሃሃ) እና ታድያ ጥንⶨሊት ዝሆንን በቡጢ እየደበደበች በሹክሹክታ ”እረ በናትህ ዝሆን አይደብርህም እንዴ ከለልከኝ እኮ…” እያለች ብትወተውት ብትወተውት አለሰማ አላት… (ዝሆን እኮ ጆሮው ትልቅ ነው እንጂ በተልቁ አይሰማም… ) ከዛ ብዚህ የተበሳጨችው ጥንቸል ከፊት ለፊቱ ሄዳ ቁጭ አለች እና ፊልሟን ኮመኮመች በማብቂያው ላይ ዞር ብላ ”አየህ አይደል የመከለል ነገር እንዴት እንደሚያበሳጭ” አለችው አሉ…

አርቲስቶቻችን የመታገን ነገር አያችሁት አየደል እንዴት እንደሚያበሳጭ… በፊልም እና ድራማ ስራ ተወጥራችሁ ልብ አላላችሁትም እንጂ እናንተ ላይ ሀዝቡ ላይ የደረሰው እገታ ዝሆኑ ጥንቸሏን ሲከልላት የነበረው አይነት ነው…!

ይሄንን እና ሌሎች እገታዎችን ለመቃወም እና መጪው አመት ብሩህ እንዲሆን ለመስበክ ነው‪#‎Blackweek‬ ብለን እየዘከርን ያለነው፤

ለማንኛውም እንሆ ፊልሙ በፖሊስ ቀጭን ትዛዝ ሲታገድ የሚያሳይ ቪዲዮ!

Abe Tokichaw

 

ሕወሃት/ኢሓዴግ ምን ያህል እንዳከረረ (ክፍል 2) – ግርማ ካሳ

$
0
0

አገር ውስጥ በሰላም የሚንቀሳቀሱ ድርጅቶች አመራር አባላት ናቸው። አብርሃ ደስታ ከአረና፣ ዳንኤል ሺበሺና ሃብታሙ አያሌው ከአንድነት፣ የሺዋስ አሰፋ ከሰማያዊ። ሐምሌ 1 ቀን 2006 ሽብርተኞች ናችሁ ተብለው ተያዙ። ጠበቃዎቻቸው በሌሉበት በድብቅ ፍርድ ቤት ቀረቡ ተባለ። ፖሊስ ዜጎችን ከመያዙ በፊት በእጁ መረጃ ሊኖረው ሲገባ፣ መረጃ ለማሰባሰብ ጊዜ ያስፈልገኛል ብሎ ለ28 ቀናት ቀጠሮ ይጠይቃል። ፍርድ ቤቱ፣ ያለምንም ማቅማማት፣ ምን መረጃ በሌለበት ሁኔታ፣ የታሳሪዎችን የዋስትና መብት ከልክሎ 28 ቀናትም እንዲታሰሩ ያዛል።

tplfከ28 ቀናት በኋላ ሃብታሙ፣ ዳንኤል እና የሺዋስ ነሐሴ 27 ቀን እንደገና ፍርድ ቤት ቀረቡ። አሁንም ፖሊስ ማስረጃ ሳያቀርብ ለ28 ቀን ሁለተኛ ቀጠሮ ጠየቀ። ፍርድ ቤቱ አሁንም፣ ምንም መረጃ ሳይመለከት፣ ፖሊስ ስለጠየቀ ብቻ፣ ዜጎች በወህኒ እንዲቆዩ አዘዘ። አምሣ ስድስት ቀናት መረጃ ሳይቀርብ ዜጎች ሕግ ያስከብራል በሚባለው አካል የሰብአዊ መብታቸው ተረገጠ። እንደገና ለመስከረም 22 ቀን ተቀጠሩ። ነሐሴ 29 ቀን ደግሞ አብርሃ ደስታ ፍርድ ቤት ሲቀርብ የተለየ ነገር አልነበረም። «ተጨማሪ ሰነድ ለማሰባሰብና ምስክሮች ለማቅረብ ጊዜ ያስፈልገኛል» ብሎ ፖሊስ በመጠየቁ ተጨማሪ 27 ቀን ይሰጠዋል።

እነዚህ የታሰሩ ወጣት ፖለቲከኞች የሰሩት አንዲት ወንጀል የለም። ወንጀላቸው ለፍትህ፣ ለሰላም፣ ለዲሞክራሲ መቆማቸው ነዉ። ወንጀላቸው አገራችውን መዉደዳቸው ነው። የሕወሃት/ኢሕአዴግ አገዛዝ ግን፣ ሕግን እንደ በተር በመጥቀም፣ ጠንካራ የሚባሉ፣ ተሰሚነት ያላቸውን ወጣት የፖለቲካ አመራሮች በማሰር፣ ሆን ብሎ የተቃዋሚዎችን እንቅስቃሴ ለማሽመድመድ እየሞከረ እንደሆነ ግን ግልጽ ነው።

ከዘጠና ሰባት በኋላ በተፈጠረው ሁኔታ «ቅንጅት ሞቷል፤ የተቃዉሞ እንቅስቃሴውም አልቆለታል» በሚል ሕወሃት/ኢሕአዴጎች ዳንኪራ ሲመቱ እንደነበረ ይታወቃል። ወ/ት ብርቱካን ሚደቅሳ የተበታተነዉን አሰባስባ አንድነት በሚል ስም ጠንካራ ፓርቲ እንዲወጣ አደረገች። የአገዛዙ ባለስልጣናት 50 ሰው አይገኝም ያሉት፣ በሜክሲኮ አደባባይ መብራት ኃይል አዳራሽ ያኔ በተደረገው፣ የመጀመሪያው የአንድነት ሕዝባዊ ስብሰባ፣ ከ5 ሺህ ሰው በላይ በመግባቱ አዳራሹ ሞላ። የአዳራሹ በር ተዘግቶ ብዙ ህዝብ እንዲመለስ ተደረገ። በአራት ኪሎ ያሉ ባለስልጣናት ደነገጡ። ሰበብ ፈልገው ወ/ት ብርቱካን ሚደቅሳን አሰሯት። ኢንጂነር ግዛቸው ሃላፊነቱን ያዙ። ነገር ግን የፓርቲው እንቅስቃሴ ተዳከመ። አንድነት ተከፋፈለ። በድጋሚ በሕወሃት/ኢሕአዴጎች ዘንድ ፌሽታ ሆነ።

አንድነት ዉስጥ እንደ አንድዋለም አራጌ ያሉ ወጣት አመራሮች መጡ። መጠነ ሰፊ ድርጅታዊ ሥራ መስራት ጀመሩ። ትንሽም ብትሆን አንድነት በአገሪቷ ሁሉ ድርጅታዊ መዋቅሩን መዘርጋት ጀመረ። የአንድነት ጥንካሬ ያሳሰበው ሕወሃት/ኢሕአዴግ እንደገና በትሩን አነሳ። አንድዋለም አራጌ፣ ናትናኤል መኮንን የመሳሰሉ ጠንካራ አመራሮች ታሰሩ።

ብዙም አልቆየም ተወዳጁ እና ተስፍ ሰጪው የሚሊየነሞች ንቅናቄ ተጀመረ። በሌላ በኩል ከመኢአድ ጋር አንድነት የሚያደርገው የውህደት እንቅስቃሴ ትልቅ መነቃቃትን ፈጠረ። የአንድነት ፓርቲ ገዢዎች ከጠበቁት እና ከገመቱት በላይ ገፍቶ ስለሄደባቸው በድጋሚ በትራቸውን አነሱ። በሚሊዮኖች ንቅናቄና በመኢአድ አንድነት ዉህደት ዙሪያ፣ ትልቅ ሚና የነበረው፣ የአንድነት የሕዝብ ግንኙነት ክፍል ሃላፊ ወጣት ፖለቲከኛው ሃብታሙ አያሌውን አሰሩት። በተለይም በደቡብ ክልል ትልቅ ድርጅታዊ ሥራ ሲሰራ የነበረዉን የፓርትቲው ምክትል የድርጅት ጉዳይ ሃላፊ ዳንኤል ሺበሺንም እንደዚሁ። የአንድነት መሪ የሆኑት ኢንጂነር ግዛቸው ፣ ሃብታሙ ከታሰረ በኋላ የሚሊየነኖምችን ንቅናቄ ማስኬድ አልቻሉም። እንቅስቃሴው ባለበት ቆመ። ወደፊትም ቆሞ የሚቀር ይመስላል፣ የአንድነት አባላትና ደጋፊዎች ግፊት አድርገው ፓርቲው ከቢሮ ወደ ሜዳ እንዲወጣ ካላደረጉት በቀር።

በአብዛኛዉ የአገዛዙን በትር የቀመሰው የአንድነት ፓርቲ ቢሆንም፣ ሰማያዊ፣ አረና እንዲሁም ሌሎችም አላመለጡም። የሰማያዊ እና የአንድነት አብሮ መስራት ፣ ብሎም መዋሃድ ፣ የአንድነት እና የመኢአድ መዋሃድ የአገዛዙ ራስ ምታቶች ነበሩ። በተቻለ መጠን ሰማያዊን እና አንድነትን ማራራቅ፣ አንድነት እና መኢአድ እንዳይዋሃዱ ማድረጉን ትልቁ ግባቸው አድርገው ነበር ሲሰሩ የነበሩት። በመሆኑም የሚቆጣጠሩትን ምርጫ ቦርድ ተጠቅመው፣ የመኢአድ እና የአንድነት ዉህደትን ለጊዜው አደናቀፉ። በሰማያዊና በአንድነት መካከል መቀራረብ እንዲኖር ይተጋ የነበረዉን የሰማያዊ ምክር ቤት ም/ሰብሳቢ የሺዋስ አሰፋንም ወደ ወህኒ ወሰዱት።


በሰሜን የሕወሃት እምብርት በሆነችዋ ትግራይ፣ የፍትህና የዲሞክራሲ ድምጽ ሆኖ ሲጽፍ የነበረው፣ የአረና አመራር አባል አብርሃ ደስታ፣ ለሕወሃቶች ትልቅ ራስ ምታት ነበር የሆነባቸው። እነርሱ ጠመንጃ ይዘዋል። እርሱ ግን ብእር ብቻ ነበረች በእጁ። በትግራይ ዉስጥ ትልቅ ንቅናቄ መፈጠሩን፣ የትግራይ ሕዝብ ከተቀረው ኢትዮጵያዊ ወገኑ ጋር አብሮ ለትግል እጅ ለእጅ መያያዙ አስደነገጣቸው። ሕወሃቶች ሊኖሩ የሚችሉት ህዝቡን ትግሬ፣ ኦሮሞ፣ አማራ እያሉ ሲከፋፍሉት ብቻ ስልሆነ፣ ኢትዮጵያዉያንንን የማሰባሰብ ፖለቲካን ይጸየፉታል። በተለይም በአብርሃ ደስታ ግፊት መቀሌ ሰላማዊ ሰልፍ ሲጠራ፣ ሰልፉ እንዳይደረግ መከልከል ሳይበቃቸው፣ የሰልፍ ጥያቄ እንደገና እንዳይነሳ በሚል ነው መሰለኝ አብርሐ ደስታን ከነሃብታሙ ጋር ወደ ማእከላዊ አስገቡት።

እንግዲህ ከላይ የጠቀስኳቸው በሙሉ የሚያሳዩት ሕወሃት/ኢሕአዴጎች ምን ያህል የተጨበጠ ሥራ የሚሰሩ የተቃዋሚ ፓርቲ መሪዎችን ማየት እንደማይፈልጉ ነው። እነርሱ የሚፈልጉት ዝም ብሎ መግለጫ የሚያወጡ፣ ዝም ብለው የሚያወሩ፣ ዝም ብለው ስብሰባ ማድረግ የሚቀናቸው፣ ከቢሯቸው የማይወጡ፣ ሕዝባዊ እንቅስቃሴ የማያደርጉ፣ ትግሉን ወደ ሜዳ የማይወስዱ መሪዎችን እና ድርጅቶችን ነው። እንደነዚህ አይነት ድርጅቶች እየጠቀሱ የዉሸት መድበለ ፓርቲ እንዳለ ለማሳየት የሚጠቀሙባቸው ድርጅቶች ናቸው።

አቶ ኃይለማሪያም ደሳለኝ «የዲሞክራሲ ስርዓት መገንባት ለኛ አማራጭ ሳይሆን ሕልዉናችን ነው» ሲሉ ብዙ ጊዜ ሰምቻቸዋለሁ። ዶር ቴዎድሮስም አዳኖምም አንድ ወቅት ከጆን ኬሪ ጎን ለጎን ቆመው፣ ኢትዮጵያ ዉስጥ ዲሞክራሲ እንደሚያብብ ነበር የነገሩን። ነገር ግን እያየን ያለው፣ ከመለስ ዘመን በባሰ ሁኔታ ሕወሃት/ኢሕአዴግ እንዳከረረ ነው። አቶ ኃይለማሪያም፣ መለስን አውት ሻይን ለማድረግ ነው መሰለኝ፣ ብዙዎችን በማሰር፣ በማስገደል፣ ሰላማዊ ተቃዋሚዎችን በመጨፍለቅ በጣም እየተጉ ናቸው።

አንድ ሕወሃት/ኢሕአዴጎች የዘነጉት ነገር ቢኖር ግን ትግሉ፣ የፖለቲክ ድርጅት መሪዎች ብቻ ሳይሆን የሕዝብ መሆኑን ነው። የሕዝብን ኃይል ደግሞ አፍነው ሊቆዩ አይችሉም። ሕዝብ ምንጊዜም አሸናፊ ነው።

ለአዲስ አበባ ነዋሪዎች በፕላዝማ ስልጠና እየተሰጠ ነው

$
0
0

• የከተማ አውቶቡስ ድርጅት 80 አውቶቡሶችን አቅርቧል

• ‹‹ምኒልክ ለኢትዮጵያ ምንም ካላበረከቱ ለምን ከእሳቸው ዘመን ጀምረን ዘመናዊ ኢትዮጵያ ብለን እንጠራለን?›› ሰልጣኞቹ

• ኦነግ በትግሉ ወቅት አልነበረም መባሉ በኦህዴድ ካድሬዎች ዘንድ መነጋገሪያ ሆኗል

የአዲስ አበባ ነዋሪዎች ከነሃሴ 27 ጀምረው በየ ትምህርት ቤቱ በፕላዝማ ስልጠና ጀምረዋል፡፡ ስልጠናውን በበላይነት የሚመራው የኢህአዴግ ጽ/ቤት መሆኑ ታውቋል፡፡ ሰልጣኞቹን ለማመላለስ ከአንበሳ የከተማ አውቶቡስ 80 አውቶቡሶችን ጠይቆ መውሰዱን ድርጅት ሰራተኛ ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡ የተለያዩ የኢህአዴግ አደረጃጀቶችን የወከሉ ካድሬዎችን ጨምሮ የሀይማኖት አባቶችም የሚገኙበት ሲሆን ለስልጠናው አበልን ጨምሮ፣ የከተማ አውቶቡስ፣ ትምህርት ቤትና ሌሎች የህዝብ ገንዘብ እየወጣ እንደሚገኝ ሰልጣኞቹ ገልጸዋል፡፡
addis-ababa-realethiopia-141
በፕላዝማ የሚሰጠው ስልጠና በታሪክ ላይ ያተኮረ ሲሆን በተለይም አጼ ምኒልክ ከፍተኛ ጥፋት እንደፈጸሙና ለዛሬይቱ ኢትዮጵያ ይህ ነው የሚባል አስተዋጽኦ እንዳላበረከቱ መገለጹ ታውቋል፡፡ በተቃራኒው የኢህአዴግ አባላት ሳይቀሩ ‹‹በታሪክ አዲሲቱ ወይንም ዘመናዊ ኢትዮጵያ ብለን የምንማረው ከምኒልክ ዘመን ጀምሮ ያለውን ነው፡፡ ምኒልክ ምንም ካላበረከቱ ለምን ከእሳቸው ዘመን ጀምረን ዘመናዊ ኢትዮጵያ እያልን እንጠራለን?›› የሚል ጥያቄ አቅርበዋል፡፡

ገዥው ፓርቲ አሸባሪ ብሎ የሚጠራቸውን ጨምሮ በሰላማዊ መንገድ የሚቃወሙት ፓርቲዎችም ወቀሳ የቀረበባቸው ሲሆን ኢህአዴግ ለኢትዮጵያ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንዳበረከተ ተገልጾአል፡፡

ስልጠናው ላይ ሌሎች ፓርቲዎች የኢህአዴግን ያህል አስተዋጽኦ እንደሌላቸው በስፋት የተገለጸ ሲሆን ለአብነት ያህልም ‹‹ኦነግ ትግሉ ላይ አልነበረም›› መባሉ በኦህዴድ ካድሬዎች ዘንድ መነጋገሪያ ሆኗል፡፡ አንድ ስልጠናው ላይ የሚገኝና ስሙ እንዳይጠቀስ የፈለገ የኦህዴድ ካድሬ ‹‹የኢህአዴግን ታሪክ ለማግነን ሲባል የምናውቀውን ታሪክ ሁሉ እየካዱ ነው፡፡ ምንም አይነት የትግል ስልት ይከተል ረዥም የትግል ታሪክ ያለውን ድርጅት ትግሉ ላይ አልነበረም በማለት ከትዝብት ውጭ የሚያስገኘው ውጤት አይኖርም፡፡ የኦህዴድ አባል ብሆንም በመዋሸት ኦነግን ልታገለው አልችልም፡፡ ይህ ጉዳይ የመወያያ ርዕስ ሆኖ መቀረቡም የሚያስገርም ነው፡፡›› ሲል ሁኔታውን ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጾአል፡፡

ምንጭ ነገረ ኢትዮጵያ

በሰመራ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችን ካድሬ ለማድረግ የተጠራው ስልጠና በማስፈራራት ተጠናቀቀ

$
0
0

አኩ ኢብን አፋር ለዘ-ሐበሻ እንደዘገበው፦

በአፋር ክልል በረእሰ መዲናው በሰመራ የሚገኘው ብቸኛው ዩኒቨርሲቲ ለ10 ቀናት ሲሰጥ የቆየው የተማሪዎች ሰልጠና ባለፈው ሰኞ ተጠናቀቋል። በስልጠናው የክልሉ የፓለቲካ መሪዎች የተገኙ ሲሆን በአጣቃላይ ሰለ መጭው ምርጫ ቅስቀሳ እንደነበረ ምንጮችን ገልፆል።
afar univercity
እንደ ምንጮቻችን ዘገባ ከሆነ ለመጪውው ምርጫ ኢህአዴግን ምረጡ ካልመረጣቹሁ ግን ስራ አታገኙም በሚል ብዙ ማሰፈራራት የበዛበት ስልጠና እንደነበረ ታውቋል፡

በዚህ አመት ከተለያዩ ዩኒቨርሲቲ የተመረቁ ተማሪዎች በሰልጠናው የተገኙ ሲሆን በተማሪዎች በኩል ለሚነሱ ወቅተዊ ጥያቄዎች ተገቢ ምላሽ ከመስጠት ይልቅ ማስፈራራትና ማስጠንቀቅ እንደነበረ ታይቷል።

በመጪው ምርጫ ኢህአዴግ እና የክልሉ ፓርቲ አብዴፓ በዩኒቨርሲቲ ተመራቂዎች ላይ ያላቸው ድፍራቻ በግልፅ በታየበት በዚህ ስልጠና በክልሉ በግልፅ ስለሚታዩ ችግሮች ላይ የሚናገሩ ተማሪዎች ስማቸው እየተመዘገበ እንደነበረ የአይን እማኞች ገልጸዋል።

በዘንድሮው ምርጫ በመላው ኢትዮጵያ ሊነሳ ስለሚችለው ሁከት ተማሪዎችን ከወዲሁ የማስጠንቀቅ ስልጣና ይመስላል ሲሉ አሰተያየት ሰጪዎች ይናገራሉ።

በኢትዮጵያ ከሚገኙ 9 ክልሎች እስከ አሁን ብዙዎቹም የሚገባቸውን ያህል ባይሆኑም በትምህርት አመስፋፋት ኋላ በመቅረት አፋር ክልል መሪነቱን ይይዛል።


አብርሃ ደስታን በተመለከተ፣ ከጠበቃ ተማም አባቡልጉ ጋር ያደረኩት ቃለ-ምልልስ

$
0
0

10407325_683812275038132_3112810637652871899_nበዛሬው ዕለት አብርሃ ደስታ ጊዮርጊስ በሚገኘው የአራዳ ፍርድ ቤት ቀርቦ የ28 ቀናት የጊዜ ቀጠሮ ተሰጥቶታል፡፡ አብርሃ ወደፍርድ ቤቱ ሁለት እጆቹ በካቴና እንደታሰሩና በአራት መሳሪያ በታጠቁ ፖሊሶች ታጅቦ ሲገባ በስፍራ የነበሩ ሰዎች ሞቅ ያለ ጭብጨባ አቅርበውለት ነበር፡፡ በፊቱ ላይ መረጋጋት እና ፈገግታ የሚነበብበት አብርሃ፣ በቻለው አቅም ሰዎችን ሰላምታ ለመስጠት ጥሯል፡፡ አብርሃ ወደችሎት ከገባ በኋላ፣ የታጠቁ ፖሊሶች ‹‹ለምን አጨበጨባችሁ? ረብሻ ፈልጋችሁ ነው፡፡›› በሚል በተለይ አንዱ ፖሊስ የያዘውን መሳሪያ አፈሙዝ ወደሰዎች በመወደር ‹‹ከግቢው ለቅቃችሁ ውጡ!›› ማለቱን ተከትሎ ሌሎች ፖሊሶችም ተመሳሳይ አቋም በመያዝ ታዳሚውን ለማስወጣት ጥረት አድርገው ነበር፡፡
በስፍራው የነበሩ የተለያዩ ሰዎች የፖሊሶችን አካሄድ በመቃወም ‹‹አንወጣም፣ ሕግ- አልጣስንም፡፡ አብርሃ ነጻ ሰው ነው ብለን ስለምናምን ለእሱ ያለንን አክብሮት እና አድናቆት ለመግለጽ እናጨበጭባለን›› በማለት ከፖሊሶች ጋር ክርክር ካደረጉ በኋላ በፖሊሶች በድጋሚ ‹‹ተፈትሻችሁ ግቡ›› በሚል አለመግባባቱ እልባት ለማግኘት ችሏል፡፡
አብርሃም፣ ከችሎት በፈገግታ ታጅቦ ሲወጣ ዝናብ እየዘነበ ነበር፡፡ ሆኖም በስፍራው ከነበሩ ታዳሚዎች ሞቅ ያለ ጭብጨባ እና ድጋፍ ተሰጥቶታል፡፡ እሱም በካቴና የታሰሩ እጆቹን ትንሽ ከፍ በማድረግ ‹‹አመሰግናለሁ›› ብሏል፡፡
እኔም የአብርሃ ደስታ ጠበቃ ለሆኑትን አቶ ተማም አባቡልጉን የተወሱን ጥያቄዎችን በማንሳት ተከታዩን ቃለ-ምልልስ አድርጌያለሁ፡፡
————————————————
ጥያቄ፡- የዛሬ የአብርሃ ደስታ የፍርድ ቤት ውሎ እንዴት ነበር?
ጠበቃ ተማም፡- የ28 ቀን የጊዜ ቀጠሮ ተሰጥቷል፡፡ ለመስከረም 22 ቀን 2007 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ተሰጥቷል፡፡
ጥያቄ፡- ለምን ተሰጠ?
ጠበቃ ተማም፡- ፖሊስ ‹‹ተጨማሪ የምስክር ቃል እቀበላለሁ፤ ተጨማሪ የሰነድ ማስረጃ እሰባስባለሁ፤ ሰነድ አስተረጉማለሁ፡፡›› ብሏል፡፡ እነዚህ ነገሮች ባለፈውም ተብለዋል፤ በፊትም ተብለዋል፡፡ እኛ ግን ተቃውመናል፡፡
ጥያቄ፡- በምን ተቃወማችሁ?
ጠበቃ ተማም፡- በሁለት ነገር ተቃውመናል፡፡ ዛሬ የሚባሉ ነገሮች በሙሉ፣ ይሄ ልጅ ከመታሰሩ በፊት መጠናቀቅ ነበረባቸው፡፡ የጸረ-ሽብርተኝነት አዋጁ በአንቀጽ 19 ላይ ‹‹አንድ ሰው ሽብር ለመስራት በቂ ምክንያት / ጥርጣሬ ካለ ..›› ይላል፡፡ ‹ሽብርን ያቋቁማል› የተባለው ጉዳይ በተራ ወንጀልነት በወንጀለኛ መቅጫ ሕጉ ላይ አለ፡፡ ስለዚህ ይህ መሆን አለመሆኑን አጣርተው ነው አብርሃ ማሰር የነበረባቸው፡፡ ያን ለማድረግ ደግሞ የምስክር ቃለ ሰምተው፤ የሰነድ መስረጃ ሰብስበው ነው ምክንያታዊ ጥርጣሬ አደረባቸው የሚባለው፡፡ ይሄንን ምክንያት አድርገው፣ ለሁለት ለሶስት ጊዜ የጊዜ ቀጠሮ ማድረጋቸው በራሱ የአሰራር ሕገ-ወጥነትን ያሳያል፡፡ ሁለተኛ ደግሞ፣ የታሰረው ምንም ማስረጃ ሳይኖር ነው፡፡ ለዚህ ማሳያው፣ የተጠረጠሩትን ይዘው፣ መረጃዎች በብርበራ የተያዙ መሆኑ ነው፡፡ ይሄ ሕገ-ወጥ ነው፡፡
ጥያቄ፡- እርስዎ በዚህ ላይ ምን አሉ?
ጠበቃ ተማም፡- ይህ ሕገ-ወጥ አሰራር ነው ብዬ አመለከትኩኝ፡፡ ይሄ የሚያመለክተው፣ ምስክር የሚጠይቁት፣ ‹‹ከእነሱ ኤሌክትሮኒክስ መሳሪያ አገኘን›› የሚሏቸው ነገሮች ከእነሱ መጀመሪያ ምንም ነገር ሳያገኙ ነው ያሰሯቸው፡፡ ይሄ ራሱ ሕገ-ወጥ ነው፡፡ ‹‹የመራራ ዛፍ ፍሬ መርዛማ ነው›› ስለዚህ ‹‹ሕገ-ወጥ ሥነ-ሥርዓት በማድረግ የሚመጣ ፍሬ በራሱ ውጤቱ መርዛማ ነው›› አልኩኝ፡፡
ጥያቄ፡- ይሄንን እርስዎ ሲሉ ዳኞች ምን አሉ?
ጠበቃ ተማም፡- ዳኛው ማስጠንቀቂያ ነው የሰጡኝ፡፡ ይሄ የተለመደ የሕግ አባባል ነው፡፡ የሥነ- ሥርዓት ሕጎች መብት ማስጠበቂያ ናቸው፡፡ እነዚህን ጥሰህ የምታገኛቸው ነገሮች በሙሉ ሕገ-ወጥነታቸውን ለማስረዳት ነው የተጠቀምኩት፡፡ ለፍርድ ቤቱም አመልክቻለሁ፡፡ ለምን? አስተሳሰሩ ሕገ-ወጥ ነው፡፡ እነዚህ ሰዎች በሽብር ተግባር ለመሰማራቸው በቂ ማስረጃ እና ጥርጣሬ ኖሮ አይደለም የታሰሩት፡፡ ያ ሁሉ የተደረገው ከታሰሩ በኋላ በቤታቸው በተደረገ ማስረጃ ነው፡፡ ይሄንን ‹‹ሕገ-ወጥነት ነው›› ስል አመለከትኩኝ፤ ለደንበኛዬም ‹‹ዋስትና ይፈቀድልኝ›› በማለት አመለከትኩኝ፡፡ ዳኛው ይሄንን ተውትና ወደእኔ ዞሩ፡፡ ማስጠንቀቂያም ሠጡኝ፡፡
ጥያቄ፡- ምን ብለው?
ጠበቃ ተማም፡- ‹‹ከዚህ በፊት በሌላ ችሎት ላይ ማስጠንቀቂያ ሰጥጬሃለሁ፤ በሄዱበት ይረብሻሉ›› አሉኝ፡፡ ያ ከዚህ ጋር ምን እንደሚያያይዘው አይታወቅም፡፡ አንደኛ፣ እኔ ማንንም ሰው ነክቼ አላውቅም፤ አልነካምም፡፡ ምክንያቱም፣ ከ14 ዓመታት በላይ በጥብቅና ሰርቻለሁ፡፡ እዚህ ፍርድ ቤት ካሉ ከብዙ ሰዎች በተሻለ ሥነ-ሥርዓት አውቃለሁ፡፡ ማንንም ሰው፣ ፖሊስንም ጨምሮ አልተናገርኩም፡፡ ከፍርድ ቤት ከወጣሁ በኋላ ፖሊሶች ይነዘንዙኝ ነበር፡፡ ‹‹እዚህ ባይሆን ኖሮ እንዲህ እናደርግህ ነበር›› እያሉ ያስፈራሩኝ ነበር፡፡ ቢቸግረኝ ‹‹ዳኞች እኛን ሊያጣሉን ነው›› አልኳቸው፡፡ በዚህ ላይ ፍርድ ቤት ጊዜ ወሰደና የ28 ቀን የጊዜ ቀጠሮ ሠጠ፡፡
ጥያቄ፡- በዛሬው ችሎት አብርሃ ያለው ነገር ነበር?
ጠበቃ ተማም፡- አዎን፡፡ ‹‹ከታሰርኩ ጀምሮ ከጠበቃዬ ጋር የተገናኘሁት አንድ ቀን ብቻ ነው›› በማለት ለችሎቱ አቤቱታ አቅርቦ ነበር፡፡ ዳኛውም ‹ ከአሁን በኋላ እንደዚህ ዓይነት ቅሬታ መስማት አልፈልግም፡፡ ከጠበቃው ጋር አገናኙት፡፡ ካልሆነ እቀጣችኋለሁ›› ብለዋል፡፡
ጥያቄ፡- በዚህ መሠረት አብርሃን መቼ ያገኙታል?
ጠበቃ ተማም፡- ነገ አርብ ነው፤ አገኘኋለሁ፡፡
ጥያቄ፡- አንድ ቀን ሲያገኙት ስሜቱ እንዴት ነበር?
ጠበቃ ተማም፡- ባለፈው ለችሎት ያመለከተውን ነበር የነገረኝ፡፡ መጎሸሙን፣ መሰደቡን፣ ሰብዓዊ መብቱ መጣሱንና አስፈራተውት መፈረሙን ነግሮኝ ነበር፡፡
ጥያቄ፡- የፍርድ ቤቱ ዳኛ እርስዎን የሚያሥጠነቅቁ ነገሮች ተናግረዋል፡፡ ተገቢ ነው? እርስዎስ በዚህ ጉዳይ ላይ ምን ተሰማዎት?
ጠበቃ ተማም፡- እኔ ስለምንም ነገር አልሰጋም፡፡ ለምን እሰጋለሁ? በሰፈሬ እና በሀገሬ ነው ያለሁት፤ ምንም አልፈራም፣ አልሰጋም፡፡ ምንም ስላላደረኩኝ ልፈራ አይገባም፡፡ እንደዛ የሚያስቡ ሰዎች ናቸው በፍራት ያለባቸው፡፡ ሕገ-ወጥ ሥራ የሚሰሩ ሰዎች ናቸው መፍራት ያለባቸው፡፡ አንተን የሚያስፈራሩ ሰዎች መፍራት አለባቸው፡፡ ለምን? በእንደዚህ አይነት ጉዳይ መፍራት ለራሴ ውርደት ይመስለኛል፡፡ ማንም ጉልበተኛ ነኝ ባይ ሁሉ፣ እንደቦዘኔ ሊያስፈራራኝ በፈለገ ቁጥር ከፈራሁና ከሰጋሁ ውርደት ነው – በዚህ ዕድሜዬ! የሆነ ሀገር ሄደህ ቢሆን እኮ፣ ‹‹ከሀገራቸው ያባርሩኛል፤ እንዲህ ያደርጉኛል›› ልል እችላለሁ፡፡ በሀገሬ ግን ለምን እሰጋለሁ፡፡ በመጀመሪያ፣ ምንም ነገር አይመጣም፡፡ ሁለተኛ፣ ነውር ነው፡፡ አንተ በሀገርህ እያለህ ማንም ሊያሠጋህ አይገባም፡፡ ምክንያቱም፣ አንዱ በሀገርህ ላይ የመኖርህ መገለጫ ሳትሰጋህ መኖር ነው፡፡ ሌላ ሀገር ያለ ይመስል አልሰጋም፡፡
ጥያቄ፡- ከዚህ ጋር በተያያዘ ጠቅለል ባለ መልኩ ማለት የምትፈልገው ነገር?
ጠበቃ ተማም፡- ለአንድ ሀገር እና ሕዝብ አብሮነት ማኅበራዊ መስተጋሩ ተጠባብቆ መኖሩ አስፈላጊ ነው፡፡ ሁለተኛ፣ ሕግ መከበር አለበት፡፡ ሶስተኛ፣ ሕገ-ወጥ ሕጎች እየበዙ ነው፣ ማብቃት አለባቸው፡፡ ስለዚህ ተከባብረን፣ ተረዳድተንና ተዋውቀን መኖር አለብን፡፡ ሁሉም ሰው አንዱ የአንዱን መብት እየጠበቀ መኖር አለበት፡፡

ወያኔና ይሉኝታ አይተዋወቁም (አንተነህ መርዕድ)

$
0
0

ጋዜጠኛ አንተነህ መርዕድ

tplf-rotten-apple-245x300ህወሃት በሻዕብያ ታዝሎ* ምኒልክ ቤተመንግስት ከገባና ኦነግንም ሆነ ሌሎቹን ጠፍጥፎ የሰራቸውን መናኛ ድርጅቶች እንኳ ሳያስቀርብ በብቻው የተያያዘው ዘረፋ፣ ሁሉን ለእኔ ብቻ ያለ ሂደቱ ያላስደነገጠው ኢትዮጵያዊ አልነበረም። ያለፉትን ስርዓቶች የተሻገሩ ሁለት አንጋፋ ጓደኛም ጋዜጠኞች ሲጨዋወቱ በቦታው ነበርሁ። አንደኛው ወያኔ ነፃ አወጣዋለሁ ከሚለው ከኩሩው ኢትዮጵያዊ ከትግራይ ህዝብ አብራክ የተገኘ ነበርና “ወንድሜ ይሉኝታ በትግርኛ ምንድን ነው የሚባለው?” ሲል ጠየቀው። “ይሉኝታ..ይሉኝታ…” እያለ ቃሉን ማፈላለግ ሲጀምርና ፈጥኖም ቃሉን ማግኘት ሲሳነው “ተወው ወንድሜ የሌለውን ነው የጠየቅሁህ ቃሉ ከሌለ ወያኔዎች ከየት ይማሩታል ብዬ ልጠብቅ” በማለት ሁላችንንም አሳቀን።

ለነገር ማሳመርያነት አነሳሁት እንጂ ይሉኝታማ ኢትዮጵያዊ ባህል ነው። ወያኔ ከመፈጠሩ በፊት ሆነ ስልጣን ከያዘም በሁዋላ በርካታ የሰሜን ወንድሞቼና እህቶቼ ጋር ኑሬአለሁ። የሚታወቁበት ትልቁ ኢትዮጵያዊ ባህላቸው ይሉኝታቸው ነው። የወያኔ መሪዎች ካባቶቻቸው ያልወረሱት ኢትዮጵያዊነታቸውንና ይሉኝታቸውን ነው። የትግራይ ህዝብ የሚታወቀው ከቀሪው ወንድሙ ኢትዮጵያዊ ጋር ተባብሮ አገሩን ሲያስጠብቅ፣ የመከራን ጊዜ በመደጋገፍ ሲያሳልፍ እንጂ ራሱን ከሌሎች አብልጦም ሆነ አሳንሶ ሲመለከት አይደለም። ከአብራኩ ወጣን ያሉት ጥቂት የህወሃት መሪዎች ግን ትናንት ተንቆ እንደነበር ከመስበክ አልፎ ከሌሎች የሚበልጥ መሆኑን በመንገር በፈጠሩለት ማንነቱ ዙርያ ለዘላለማዊ ስልጣናቸው ጭፍን ድጋፍ እንዲሰጣቸው ያዘጋጁታል። ከተቃወማቸውም ራስን ዝቅ በማድረግ እንደተሳተፈ በመወንጀል እንዲያፍርበት ሊያደርጉ ይሞክራሉ። ለዚህም ነው በርካታ የትግራይ ምሁራን አንድም በፍርሃት ያለዚያም እነመለስ ያስቀመጡትን የማይጠቅም ይበላይነት ምናብ መዳፈር አቀበት የሆነባቸው። የተያዘው መርዘኛ አካሄድ ልጆቻቸው ነገ ቀና ብለው እንዳይሄዱ እንደሚያደርግ ሳያጡት ቀርተው አይደለም።

ሂትለር የአርያንን ዘር ንፁህና ከማንም በላይ ነው ሲል እውነት ለጀርመኖች ትልቅነት አስቦ አልነበረም። ጠቅልሎ የያዘውን ስልጣን ለማቆየት የዋህ ጀርመኖች በጭፍን እንዲደግፉትና እንዲታወሩ፣ በፈጠረላቸው የምዕናብ ዓለም እየማለሉ እውነቱን እንዳያዩ በመሆኑ ይህንን ያልደገፉትን የበላይነታቸውን የሰበካቸውን ጀርመኖች ሳይቀር አይቀጡ ቅጣት አድርሶባቸዋል። ጀርመኖች ከውድቀታቸው በኋላ በዓለም ፊት አንገታቸውን ቀና እንዳያደርጉ፣ አባቶቻቸው በሠሩት ስህተት ልጆቻቸው እንዲያፍሩበትና ይቅርታ እንዲጠይቁ ተደርገዋል። በጊዜው “ኸረ ይህ ነገር ትክክል አይደለም፣ ሰው ሁሉ እኩል ነው፣ ጀርመኖች ከሌላው አንበልጥም፣ ሌላውም ከኛ አያንስም፣ በሌሎች ላይ የሚሰራውን ግፍ አንቀበልም” የሚል እውነት ገኖ እንዳይወጣ በዚህ መርዘኛ የዘር ልክፍት የተበከሉ ውርጋጦች ጩኸት ሰማየ ሰማያትን ሞልቶ፣ ሰይፋቸው ማንንም ተቃዋሚያቸውን ለመቅላት ሲወናጨፍ በፍርሃትና ባርምሞ የተቀመጡ ብዙ የሆኑትን ያህል ታላላቅ የተባሉ ምሁራን ሂትለርን ለመሰለ መሃይም በአገልጋይነት ተንበርክከዋል። እነዚያ አገልጋዮች እስከ ዛሬ ከየተደበቁበት እየታደኑ በዘጠና ዓመታቸው ሳይቀር ፍርዳቸውን ሲያገኙ የዛሬ ጀርመኖች ዓለምን ተባበሩ እንጂ ትክክል ናቸው ብለው ከጎናቸው አልቆሙም።

ወያኔዎች ስልጣን በያዙ ማግስት ጎንደር ከተማ ጣልያን የተከለውን የበሰበሰ አሮጌ ጄኔሬተር ነቅለው ወደ ትግራይ ሲወስዱ ለትግራይ ህዝብ ይጠቅማል ብለው አልነበረም። ገና ሲነቀልና ሲጫን ፍርስርሱ የሚወጣ መሆኑን ያውቁታል። ዋናው ዓላማቸው ዮሃንስ አንገታቸውን ሰጥተው ያጸኑትን የጎንደርና የትግራይ ህዝብ የቆየ አንድነት ለመበጠስ ነው። ስልጣን ላይ ያሉትን ወያኔዎች እንተውና በጊዜው የዚህ እኩይ ተግባር ተዋናይ የነበረውን ስዬ አብርሃን “ለምን ጥቅም ነበር የወሰዳችሁት?” ብሎ በመጠየቅ እውነቱን የሚናገር ከሆነ መስማት በተቻለ ነበር።

ሰሞኑን ኢሳት የምስራቅ አፍሪካ በይነ መንግስታት (ኢጋድ) ተወካዮች ሁሉም የትግራይ ተወላጆች ናቸው ሲል ዜና አቅርቧል። ዜና የሆነው ለኢሳት ነው? ወይስ ለኢትዮጵያ ህዝብ? ብሎ መጠየቅ የተገባ ነው። በውጭ ለሚኖረው ኢትዮጵያዊ እንኳ ዜና መሆን አይችልም። ምክንያቱም በየትኛውም ውጭ በሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ ጉዳዩን ለማስፈፀም የሄደ ሁሉ ኤምባሲው በማን እንደተሞላ በቀላሉ ያየዋልና። አውሮፓና አሜሪካ ቤት የሚገዙት፣ ቢዝነስ የሚከፍቱት አዳዲስ ስደተኞች እነማን እንደሆኑ ያውቀዋልና። አባዱላ ገመዳና ጥቂት ኦህዴዶች የተወረወረችላቸውን ፍርፋሪ ሲሻሙና ሲሻኮቱ ቀልባችን ተስቦ ሳለ ድፍን ኦሮምያን መሬት ቱባ ህወሃቶች ወስደውት ብታገኙ፣ የጋምቤላን ደን ከነነዋሪው ጨፍጭፈው ዐይናችንን ካራቱሪ ላይ ተክለን ሳለ በነጋታው ባንድ ቋንቋ ተናጋሪ ህወሃቶች ሁሉም መሬት ተይዞ ብናገኘው፣ የአዲስ አበባ ክፍት ቦታ ሆነ ነዋሪው ያለበት ለልማት ነው ተብሎ በማፈናቀል ጄኔራሎቹና ትልልቅ ካድሬዎች የሰማይ ጠቀስ ፎቅ ባለቤት ቢሆኑና አዲስ አበባ ጠብባቸው ከኦሮምያ ዞን ገበሬ ማፈናቀል ቢያምራቸው የተቃወማቸውን አምቦ ላይ ቢጨፈጭፉ ለምን አዲስ ይሆንብናል? የመለስን ቦታ ማን ይይዘው ይሆን በሚል እሳቤ ሰው ሁሉ ስራ ሲፈታ ያለ ጠቅላይ ሚኒስትር አቅራቢነት ከትግርኛ ተናጋሪዎች ብቻ ጄኔራሎች ሲሾሙ ለምን እንደነግጣለን? ሃያ ሶስት ዓመት ሙሉ የሚደረገው አንድ ዓይነት ነገር ሆኖ በየቀኑ ለምን ዜና ይሆናል? የተያዘው ነገር የትግራይ ህዝብ ከቀሪው ኢትዮጵያዊ የተለየ ተጠቃሚ በማስመሰል መለያየትና ያለነሱ ስልጣን ላይ መቆየት የትግራይ ህዝብ ህልውናው እንደማይጠበቅ በማስፈራትና በማሳመን ሙሉ ድጋፉን እንዲሰጣቸው ነው። ልክ ሂትለርና ጓዶቹ እንዳደረጉት። ከትግራይ ህዝብ መካከል ለህሊናው፤ ለእውነት የቆመ ብቅ ሲል ይቀጠፋል። አብርሃ ደስታን ያዩአል። ለሌሎቹ ለህሊናቸው የተገዙ ትግርኛ ተናጋሪዎች ሊተላለፍ የተፈለገ መልዕክት ነው።

ከአስራ አምስት ዓመት በፊት ከከርቸሌ ፍርድ ቤት ከሚያመላልሱን ህወሃቶች አንዱ ጠጋ ብሎ ያዋራኝ ነበር። የምንጽፈው ሁሉ የትግራይ ህዝብ የበለጠ ተጠቃሚ እንደሆነ አድርገን መሆኑን ሊነግረኝ ሞከረ። እኛ የምንጽፈው ሆነ የምንናገረው ከዚያ በተቃራኒ እንደሆነ አስረዳሁት። የተወያየነው ብዙ ቢሆንም ጭብጡ እንዲህ ነበር። እያንዳንዱ የትግራይ ቤተሰብ አንድና ሁለት ልጆቹን ለዚህ ትግል ገብሯል፣ የጋገራትን ቂጣ፣ የቆላትን ጥሬ አካፍሏችሁ ለዚህ በቅታችኋል። ከበርካታ ሺህ ወያኔዎች የጥቂቶች ህይወት ብቻ ተቀይሯል። እንኳን ጠቅላላው የትግራይ ህዝብ ይቅርና አንተና መሰሎችህ እንኳ ይዛችኋቸው የመጣችሁልንን መኳንንትና እነሱ የሚያስሩንን ከመጠበቅ የምትገላገሉ አይመስለኝም። አይደለም ያንን ሁሉ በወጣህ በወረድህበት ገደላገደል የሚኖሩ ትግራዋይን፤ የቅርብ ቤተሰብህን የሚያረካ ነገር የማድረግ አቅም የለህም። አንተና አለቆችህ በሌሎች ኢትዮጵያውያን በምትፈጽሙት ግፍ የትግራይ ህዝብ ርሃብ ቢጠናበት እንኳ ተሰድዶ ነፍሱን ማትረፍን እንዲፈራ፣ ሌሎችም በጥርጣሬ እንዲያዩት አደረጋችሁ። የወንድማማችነት ገመዱን በጠሳችሁ። በማለት ስሞግተው አንገቱን ከደፋበት ማቅናት ተሳነው። እውነቱ በርግጥ ገዝፎ ታይቶት ይሆን? ያ አጃቢዬ ዛሬ አንድም እንዳልሁት አሁንም የጌቶቹና የእስረኞች ጠባቂ ነው። ቀንቶት ሚሊየነር ከሆነም የሱ ኑሮ ጥርሾና ቆሎ እያካፈሉ ነፍሱን ላሳደሩት የትግራይ ገበሬዎች አይተርፍም፤ አስር የሚሆኑ ቤተሰቦቹን ረድቶ ከሆነም ትልቅ ነገር ነው። አዲስ በለመደው ኑሮ ተውተብትቦ ሲኳትን የቀሪውን ትግራይ ህዝብ መከራ ያከብደዋል። ሃውዜንና በሌላም የትግራይ አካባቢዎች ላይ የተጨፈጨፉ ሰዎችን አፅም ከርሻው እየለቀመ ወደ ጎን አድርጎ ዝናብ ጠብቆ በደንጋዮች መካከል በምትበቅል እፍኝ የማትሞላ እህል የሚንጠራወዝ የትግራይ ብዙሃን ከርሃብ አሁንም አልተገላገለም። ከዚችውም ኑሮው የአካባቢ የህወሃት ካድሬዎች ስቃይ ይታከልባታል።

ይህ ይሉኝታ ያጣ የወያኔዎች ዘረፋ ይዋል ይደር እንጂ ራሳቸውን መልሶ ይውጣቸዋል። ስግብግብ ፍላጎታቸው ዳርቻ ስለሌለው መከራው የበዛበት ህዝብ አሁንስ በቃኝ የሚልበት ምልክቱ እየታየ ከመሆኑም በላይ ዳር ለዳር ፍርፋሪ በመልቀም የደለቡ የኦህዴድ፣ የብአዴን፣ የደህዴን፣ የሶማሌ፣ የአፋር፣ የጋምቤላ ወዘተ ካድሬዎች ፍርፋሪው እጅ እጅ ብሏቸው ከዋናው ሞሰብ ወያኔዎች ጋር በእኩልነት መቋደሱ ስለሚያምራቸው መገፋፋቱ መናናቁ እየተከሰተ ነው። የትግራይ ህዝብም ሆነ ልሂቃኑ አዳጋው ማንጃበቡን ለማየት የሚሳናቸው አይመስልም። በተለይ ምሁራኑ ሳይማር ያስተማራቸውን ህዝብ ከወንድሞቹ እንዳይቆራረጥ በማስተማርና ድምፃቸውን በማሰማት መታደግ ያለባቸው ጊዜ አሁን ነው።

በረሃ ላይ በርካታ የትግራይ ልጆችን ሲጨፈጭፉ ምንም ያልተሰማቸው ወያኔዎች ባለፉት ሃያሶስት ዓመታት በቀሪው ኢትዮጵያዊ ደም የጨቀየ እጃቸውን በትግራይ ህዝብ ላይ ሊያብሱ ሲሚክሩ ዝም ሊባሉ አይገባም። ሰሞኑን በኢሳት እንደተከታተልነው ያንን ሁሉ ግፍ የሰሩት በጣት የሚቆጠሩት የህወሃት ባለስልጣናት በስዊድን ዓለም አቀፍ ጦር ፍርድ ቤት ክሳቸው ሊመሰረት እንድሆነ ሰምተናል። አርከበ እቁባይ፣በረከት ስምዖን፣አባዱላ ገመዳ፣ ሳሞራ የኑስ፣ አባይ ፀሃዬ፣ጌታቸው አሰፋ፣ ሌ/ጄ ታደሰ ወረደ፣ ሃሰን ሺፋ፣ ሙሉጌታ በረሄ፣ ነጋ በረሄ፣ ወርቅነህ ገበየሁ፣ ኮማንደር ሰመረ…ስማቸው ይፋ ሆኗል። እነዚህና ሌላ ጥቂት የህወሃት ከፍተኛ ወንጀለኞች ዓልም አቀፍ በሆነ መልኩ ተጠያቂ እንዲሆኑ መቅረቡ ብቻ አይደለም ትልቁ ድል። ከአሁኗ ሰዓት ጀምሮ ህዝቡ ዐይኑን ገልጦ የሰሩትን ሁሉ ወንጀል በመከታተል ለፍርድ ሊያቀርባቸው ቆርጦ መነሳት መጀመሩም ነው። ከህዝብ በግፍ የጋፈፉት ገንዘብ የሰሩትን ሃጢያት ሊሸፍንላቸው ካለመቻሉም በላይ በየትኛውም የዓለም ክፍል ቢሄዱ ከተጠያቂነት አያመልጡም። የሂትለር ናዚዎችም ከሰባ ዓመት በፊት በሰሩት ወንጀል ፍርዳቸውን ለማግኘት እስካሁኗ ሰዓት እየተለቀሙ ነው። በስሙ የተነገደበት የትግራይ ህዝብ እነሱን ደግፎ የራሱን ታሪክ አያበላሽም። ለልጆቹም ሃፍረትን አያወርስም።

በፍርሃትና በጥቅም ወያኔን የተጠጋ ሁሉ ከሚወድቅ ስርዓት ጋር አብሮ መውደቅ እንደሌለበት ማገናዘብና ወደ ህዝብ መቀላቀል ያለበት ጊዜ አሁን ነው። አምባገነኖች በተለይም ወያኔዎች ይሉኝታ የሚባል ነገር የላቸውም። ነገሮች ሲከፉ ቆይተው ለመስዋዕት የሚያቀርቡት ቢኖር በአድርባይነት የተጠጋቸውን ነው። ከራሱ በላይ ለሚያገለግለው እቃ ክብር የሚሰጥ ማን አለ? ኦህዴዶች፣ ብ አዴኖች፣ ደህዴዶች፣ አፋሮች፣ ሶማሌዎች፣ ጋምቤላዎች ወዘተ እየተባላችሁ ለፍርፋሪ የተጥጋችሁ የሞሰቡ ዋና ተቋዳሽ አለመሆናችሁን አውቃችሁ ከዘመናዊ ባርነት ራሳችሁን አውጡ።

ቀሪው ኢትዮጵያዊ እነሱ በፈጠሩልን መከፋፈል ሆነ በራሳችን ድክመት ያሳለፍነው መከራ ተጠያቂዎች ነን። ሁሉም በተደራጀ መልኩ ሆነ በግሉ ጠጠሩን ወደ አንድ አቅጣጫ ይወርውር። ወደ ዘረኛው ወያኔ። ያ ጠጠር ናዳ ሆኖ የማይገደብ ሃይል ይሆናል። ከአሁን በኋላ ከወያኔ ውጭ በሌላው ኢትዮጵያዊ ላይ ጠጠር በመወርወር ጊዜና አቅሙን የሚያባክን ካለ ከውያኔ አረመኔዎች አካል እንደሆነ ይቆጠራልና።

የኢትዮጵያ ህዝብ በልጆቹ ትግል ነፃነቱን ይጎናጸፋል!

ጸሃፊውን በ amerid2000@gmail.com ማግኘት ይችላሉ

አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ እንዲፈቱ የሚጠይቅ አውሮፓ አቀፍ የተቃውሞ ሰልፍ በለንደን ተካሄደ

$
0
0

Andargachew Tsige.jpg2ነሃሴ ፴(ሠላሳ)ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ከመላው አውሮፓ የተሰባሰቡ ኢትዮጵያውያን የተገኙበት ይህ የተቃውሞ ሰልፍ እጅግ ደማቅ መሆኑን ወንድማገኝ ጋሹ በስልክ ገልጿል። የግንቦት7 ዋና ጸሃፊ በየመን የጸጥታ ሃይሎች ተይዘው ተላልፈው ከተሰጡበት ጊዜ ጀምሮ የኢትዮጵያ መንግስት ሰብአዊ መብታቸውን በመግፈፍ በኢትዮጵያውያን እንዳይጎበኙ ከልክሏል። አብዛኛውን ስራቸውን እንዳጠናቀቁ በተደጋጋሚ ሲናገሩ የነበሩት አቶ አንዳርጋቸው ወደተለያዩ ቦታዎች በሌሊት እየተዘዋወሩ ምርምራ እየተደረገባቸው መሆኑን የሚደርሱን መረጃዎች ያመለክታሉ። የኢትዮጵያ መንግስት አቶ አንዳርጋቸውን ለመያዝ ከፍተኛ ገንዘብ ለየመን የጸጥታ ሃይሎች መክፈሉን መዘገባችን ይታወሳል።

Source:: Ethsat

በአንድነት ፓርቲ ውስጥ ራሳቸውን ከድርጅቱ የሚያገሉ አባላት እየጨመሩ ነው።

$
0
0

UDJ“ግዜ ከማባከን ውጭ አሁን ባለው ሁኔታ ለውጥ ማምጣት አይቻልም። ” አቶ ጸጋዬ አላምረው

አንድነት ፓርቲ ከተመሰረተበት ግዜ ጀምሮ የሂሳብ ክፍል ሃላፊ በመሆን ሲያገለግሉ የቆዬት አቶ ፀጋዬ አላምረው ከነሐሴ 30/12/2006 ዓ.ም ጀምሮ ከሂሳብ ክፍል ሀላፊነታቸው ራሳቸውን በፈቃዳቸው ማግለላቸውን ገልፀዋል፡፡

የአንድነት ፓርቲ የጀርባ አጥንት በመባል በትግል አጋሮቻቸው የሚነገርላቸው አቶ ፀጋዬ አላምረው ራሳቸውን ከሃላፊነት ያገለሉበት ምክንያት አሁን ባለው ሁኔታ ፓርቲው ለወጥ ያመጣል ብለው እንደማያምኑና በዚህ ሁኔታ መቀጠሉ ግዜ ከማባከን ውጭ ተጨባጭ ለውጥ ስለሌለው ራሳቸውን ለማግለል መገደዳቸውን ገልፀዋል፡፡የፓርቲው ፕሬዝደንት አዲሱን ካቢኔ ሲያቋቁሙ በተሸሙት ካቢኔዎች ለውጥ ይመጣል ብለው እንደማይጠብቁ ለምክር ቤቱ ማስረዳታቸውም አይዘነጋም፡፡

Yared Amare ከአንድነት ፓርቲ እንደዘገበው

 

በወያኔ ስር የሚገኘው የመከላከያ ሰራዊት፣ የወያኔ አገልጋይ ኢሕአዴግ፣የአፋኞችና የነፍሰ ገዳዮች ምሽግ- የወያኔ ደህንነት

$
0
0

ዓምን ዘለቀ

ዋና ጸሃፊያችንና  የትግል ዳችን  አንዳርጋቸው ጽጌ                      —PDF click here 

neamen zeleke

ነዓምን ዘለቀ

የንቅናቄአችን ዋና ጸሃፊና የትግል ጓዳችን  አንዳርጋቸው ጽጌ  በየመን ትብብር በፋሽስታዊ ወያኔ አፋ   ኞች  እጅ መውደቅ ያስቆጣው የኢትዮጵያ ሕዝብ ባሳየው ወገናዊነት ልባችን ተነክቷል። የአንዳርጋቸው መታሰር ይቆጨናል፤ እየደረሰበት ያለው ስቃይ ያንገበግበናል፤ የሱን አይነት ብርቱ፣ ቆራጥ፣ አስተዋይና ብቃት ያለው ታጋይ ትግሉ ማጣቱ ይጎዳናል:: አንዳርጋቸው በሳል የፖለቲካ ሰውና ቆራጥ የተግባር ታጋይ ብቻ አይደለም። በግል ለማታውቁት በበርካታ የእውቀት ዘርፎች በጥልቀት ያነበበ፤ ፍልስፍና፣ ሊትሬቸር፣ ሲኒማ የሚወድና ህሊናው በዕውቀት በከፍተኛ ደረጃ የበለፀገ ነው። የሰው ልጅ መከራ፣ በደልና ስቃይ እስከ አጥንቱ ይሰማዋል። ዱባይ ላይ ከአመት በፊት ስላገኛት ኢትዮያዊት የነገረኝ ሲቃ እየተናነቀው ነበር።ልጅቷ ሲያገኛት ያለማቋረጥ ታለቅሳለች፤ ምን እንደሆነች ቢጠይቃት ለመናገር ባትፈቅድም አጥበቆ ሲይዛት እንደተናገረችው፤ ተቀጥራ በምትሰራበት  የቤቱ ባለቤት ሽማግሌ አረብና አራት ወንድ ልጆቹ በየገዜው ተራ በተራ ደፍረዋታል። የሚያስነባት ይህ ነበር። አንዳርጋቸው “የኢትዮጵያውያን መከራና ውርደት መቼ ነው የሚያበቃው” በሚል ነበር ሲቃ እየተናነቀው ያጫወተኝ።

አንዳርጋቸው የንዋይና የስልጣን ፍቅር የለበትም። ፍላጎቱ ያ ቢሆን ኖሮ ዛሬ  ወያኔ ከሰበሰባቸውና ከፍተኛ ደረጃ ላይ ከሚገኙ የወያኔ ሎሌዎች የተሻለ ደረጃ ላይ ባገኘነው ነበር። በምንም መለኪያ በሱ ደረጃ ብቃት፣ ምሁራዊ ብስለትና ስብዕና  የተላበሡ እንደሌሉባቸው ግልጽ ነው። አንዳርጋቸው የመረጠው የፍትሕ፣ የነጻነትና የእውነትን መንገድ ሲሆን እሱ የመረጠው ከህሊናው ጋር መኖርን ነው።  ለዚህም ነው ስልጣን እና ገንዘብን ገፍቶ፣ የአውሮፓን ምቾት ትቶ፣ በርሃ ወርዶ አፈር ላይ እየተኛ በርካታ ታጋዮችን አስተምሮ ትግሉን ጠንካራ መሰረት ላይ የተከለው – ትግሉን መስመር አስይዞ ዛሬ በፋሺስቶች እጅ ቢወድቅም።

ፋሽስቶቹ ወያኔዎች በተለመደው ድንቁርናቸው ያቀዱትና የአለም አቀፍ ህግን ጥሰው የሄዱበት የብልግናና የውንብድና  መንገድ እሱን በማፈን ነጻነትና  ፍትህ የጠማውን የኢትዮጵያ ህዝብ አንገት እናስደፋለን፣ ቅስም እንሰብራለን፣ ታጋዮችና ትግሉን እናዳክማለን፣እናመክነዋለን ከሚል ስሌት  ነበር። በተቃራኒው ኢትዮጵያውያን በሀገር ውስጥም በውጭው አለም ከዳር ዳር በከፍተኛ ቁጣና ቁጭት እንዲንቀሳቀሱ እያደረገ፤ ለመራራ ትግል እንዲዘጋጁና ለመስዕዋትነት እንዲቆርጡ እያነሳሳ ይገኛል። <<እኔም አንዳርጋርጋቸው ጽጌ ነኝ>> በሚል በሺህ የሚገመቱ ኢትዮጵያውያን ትግሉንም ንቅናቄአችንንም እንዲቀላቀሉ እያደረገ ነው።  ዛሬ ብዙ ሺዎች የአንዳርጋቸው ጽጌን ፈለግ ተከትለዋል፡፡ በአጭር ጊዜ ውስጥ ሚሊዮኖች የነጻነት፣ የእኩልነት፣ የፍትህ ጠበቆችና ታጋዮች ሆነው የፋሽስታዊውን የወያኔን ስርዓት በሁሉም መንገዶች እንደሚፋለሙ አፍታም ጥርጥር የለንም። በግንቦት 7 በኩል  እልሃችን፣ ቁጭታችን፣ ጽናታችን፣ ቁርጠኝነታችን እጥፍ ድርብ እንዲሆን አድርጎናል። እኛም ግንባራችችንን ሳናጥፍ የተጀመረውን ትግል ከግብ ለማድረስ በቁርጠኝነት ተነስተናል። በዛሬው እለትና በሚቀጥሉት ሁለት ሳምንታት ንቅናቄያችን በመላው ዓለም በ27 ከተሞች ከሚያደርገው ህዝባዊ ስብስባዎች አንዱ በሆነው በአትላንታ ከተማ በመካከላችሁ የተገኘሁት ኢትዮጵያ ሀገራችንንና ህዝባችን የሚገኙበትን የምታውቁትን እጅግ አስከፊ ሁኔታ  ለመደጋገም አይደለም።

የዛሬው ስብሰባ ዋና አላማና ትኩረት ትግሉ ወደ አንድ ሌላ ወሳኝ ምዕራፍ መሸጋገሩን በተመለከተ የጋራ ግንዛቤና የትግል አቅጣጫ እንዲኖረን ለመመካከር ነው ሲሆን፤ ሁሉም የዚህ ትግል ንቁ ተሳታፊና አባል እንዲሁም ደጋፊ በመሆን ምን አይነት ተግባራዊ የትግል እንቅስቃሴዎችን ማድረግ እንደሚገባን ሁላችሁም ወስናችሁ እንድትንቀሳቀሱ ለማስገንዘብና ለልዩ ልዩ የህብረተሰብ ክፍሎችም የንቅናቄአችንን ጥሪ ለማቅረብ ነው።

ዘረኛውና ዘራፊው የወያኔ አርነት ትግራይ ስርዓት

የኢሕአዴግ/ኦህዴድ ከፍተኛ ካድሬና የካድሬዎች አሰልጣኝ የነበረውና በልዩ ልዩ ከፍተኛ መንግስታዊ ሃላፊነቶች  ስርአቱን  ያገለገለው አቶ ኤርሚያስ ለገሰ ከጋዜጠኛ ሲሳይ አጌና ጋር በኢሳት ቴሌቪዥን እና ራዲዮ ያደርገውን ሰፊ ቃለ-ምልልስ  የተከታተላችሁ ይመስለኛል። አቶ ኤርሚያስ ለገሰ በርካታ ሃቆች፣ መረጃዎችና ቁም ነገሮችን በአካተተበት “የመለስ ትሩፋቶች” በሚል ርእስ ያሳተመው የመጀመሪያ መጽሐፉ በቨርጂንያ በተመረቀበት ወቅት በስፍራው ተገኝቼ  ኤርሚያስ ሲናገር የሰማሁዋቸውና ለዚህ ስብሰባ ፋይዳ አላቸው ብዬ የወስድኳቸውን እዚህ ለመጥቀስ እወዳለሁ፡፡

“ስርዓቱ የኔ ነው እንድትል፤ የኔነት ስሜት (Sense of Belongingness) እንዲሰማህ አያደርግም።  የወያኔ/ህወሃት ዋና ተግባሩ ዘረፋ ነው”።  “ኢህአዴግ  በጥራትም፣ በጽናትም፣ በብቃትም እዚህ ግባ የሚባል ድርጅት አይደለም” የሚሉ አስተያየቶችን ሰንዝሮ ነበር

የወያኔን አገዛዝ ምንነት አሁንም ድረስ በአግባቡ ላልተረዱ ብዙ መረጃዎችና ሃቆች ያካተተ መጽሀፍ ነው። ባለራዕይ ከሚሉት ከቀድሞ የወያኔ ቁንጮ ጀምሮ በቀለኞች፣ ቂመኞችና ዘረኞች መሆናቸውን ይበልጥ ተረድተንብታል። የአብዛኞቹን የወያኔ መሪዎችና አባላት እኩይነት፣ ዘራፊነት፣ አጭበርባሪነት፣ የስርዓቱን እጅግ የወረደና የዘቀጠ ምንነት፣የመሪዎቹን ርካሽነት፣ ጭካኔአቸውን፣ ለከት የሌለው ስግብግብነታቸውን፣ በስርዓቱ ውስጥ የነገሰውን አድርባይነት ገላልጦ አሳይቶናል። እጅግ የወረደ ስብዕና ባላቸው ጨካኝና ርካሽ ሰዎች እጅ ሀገራችን ኢትዮጵያ እንደወደቀችም ተገንዝበናል። ስርዓቱን ጥለው ከወጡት የቀድሞ ባለስልጣናት ያልሰማነውን በርካታ ውስጠ ድርጅታዊ ምስጢሮችን ያካተተ ትልቅ ግንዛቤ የሚያስጨብጥ ታሪካዊ ሰነድ ጭምር በመሆኑ ሁሉም ኢትዮጵያዊ ሊያነበው የሚገባ መጽሐፍ ነው የሚል እምነት አለኝ።

እነዚህን  ላለፉት በርካታ የትግል አመታት ካጠራቀምናቸው መረጃዎችና ሃቆች ጋር ስንደምራቸው የዚህ ዘረኛና  ለከት የለሽ ስግብግብ የወያኔ አገዛዝ ማንነት መፈተሽ የሚገባው በይፋ (officialy)  ባስቀመጠውና በብልጣ ብልጥነት በሚነግድባቸው – አብዮታዊ ዴሞክራሲ፣ ልማታዊ መንግስት፣ የትራንስፎርሜሽን እድገት ወዘተ – ርዕዮቱ ሳይሆን በተግባር በሚሰራበት (Operating) ርዕዮት ሊሆን ይገባዋል፤ ይህም ተግባራዊ ርዕዮት ዘረኝነትን መሰረት ያደረገ ወያኔዎች የተያያዙት መንግስታዊ ዘረፋ ነው። ወደ ስልጣን እስኪመጡ ከደርግ/ኢሰፓ ጋር በሚታገሉበት ወቅት በጠባብ ብሄረተኝነትና በዘረኝነት የታጀለ ቢሆንም፣ ቢያንስ በወቅቱ አንግበውት የነበረው ፍትህ፣ እኩልነት፣ የብሄር ብሄረሰቦች መብት ወዘተ የሚሉ ነበሩት። ዛሬ ግን ትርጉም አልባ መፈክሮች መሆናቸውን የወያኔዎች 23 ዓመታት ተግባሮቻቸውና አድራጎቶቻቸው በይፋ ይመሰክሩባቸዋል።

የፋሽስቱ ወያኔ ዘረኝነት ከህመም ወደ ነቀርሳ (Cancer) የተለወጠ መሆኑ ግልጽ ነው። ከ23 ዓመታት በኋላም የመከላከያ ሰራዊቱን ዕዝ ወሳኝና ቁልፍ ቦታዎች ከላይ እስከታች 95 በመቶ፤ የደህንነቱ መዋቅሩም 90 በመቶ እንዲሁም የሀገሪቱን ኢኮኖሚ 50 በመቶ ኤፌርት የሚባለው የህወሃት ግዙፍ ኩባንያዎች ስብስብ (Conglomerate) ተቆጣጥሯል። የህወሃት አባላትም በቤተሰብ፣ በዘመድ-አዝማድ የተያያዙ  በሰፊው የትግራይ ህዝብ ስም የሚነግዱ የትግቋንቋ ተናጋሪዎች ሁሉንም በበላይይዘዋል። ይህ አዲስ ዘረናና ዘርራፊ ገዥ ቡድን (oligarchy)  የዳበረበት፣ ፍጹም የሆንር ኢፍትሃዊ  የስልጣን፣ የጥቅም፣ የስራ፣ የትምህርት፤ የኢኮኖሚ ወዘተ የነገሱበት፤  አድሎ  የተንሰራፋበት  መሆኑን  የምታውቁትና  የኢትዮጵያ ህዝብም  የሚኖርበት ሃቅ ነው ።

አሸባሪው የወያኔ አገዛዝ በመጠነ ሰፊ ቅራኔዎች ተቀስፎ የተያዘ፣ ደካማና ከፍተኛ ጭንቀት ውስጥ የገባ ስርዓት ነው። መሪዎች እርስ በርስ የማይተማመኑ፣ የጎሪጥ የሚተያዩ፣ የሚናናቁ ስለመሆናቸው ንቅናቄያችን በርካታ መረጃዎች አሉት። ለስልጣን ያላቸው ስግብግብነትና ዘራፊነታቸው ስላስተሳሰራቸውና ስላያያዛቸው ብቻ በጉልበት፣ በአፈና በሽብር የሚገዙ ናቸው። ራሱ ባወጣው ህገ መንግስት ውስጥ የደነገጋቸውን ዩንቨርሳል ዲክላሬችን ኦፍ ሁማን ራይትስና ሌሎች ህጎችን ሁሉ በየእለቱ እየረገጠ የቀጠለ ስርዓት ነው። በህዝብ ዘንድ ተቀባይነት (Legitimacy) የሌለው መሆኑን የስርዓቱ መሪዎች ያውቁታል። የዚህን ስርዓት ደካማነትና የፈጠራቸውን ዘርፈ ብዙ ቅራኔዎች የሚመሰክሩት ስርዓቱን ጥለው የሚወጡት  ብቻ አይደሉም፤ በቅርብ ጊዜ አዲሱ ለገሰ የሚባለው መሪ ካድሬ የፃፈውንና በኢሳት የቀረበውን ብዙዎቻችሁ የሰማችሁ ይመስለኛል። ስርዓቱ ከፍተኛ ችግር ውስጥ እንደወደቀ ከፍተኛ የሆነ የአመራር እጦትና በርካታ ሌሎች ችግሮች እንዳሉበት፤ ከግንቦት 7ና ከኦነግ ጋር የሚሰሩ የብአዴንና የኦህዴድ አመራሮች እንዳሉ ወዘተ አዲሱ ለገሰ ለጠቅላይ ሚኒስትሩ አማካሪዎች ባቀረበው ሪፖርት ዘርዝሯል። ይህን ተከትሎም በመላው አገሪቱ የሚገኙ 350ሺህ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችን ኢህአዴግ  የሚባለው የወያኔ መገልገያ ድርጅት አባል ለማድረግ አስገዳጅ ስልጠና መጀመሩን ታውቃላችሁ፡፡

የወያኔ/ህወአት አገልጋይና መሳሪያ የሆነው  ኢሕአዴግ

ወያኔዎች ኢህአዴግ በሚባለው ጭንብላቸውና መሳሪያቸው ከዚህ ቀደም እንዳደረጉት አሁንም ልዩ ልዩ የህብረተሰብ ክፍሎችን አስገድዶ የፓርቲ አባል የማድረጉ ሂደት  እድሜያቸውን የሚያራዝም የሚያድን እንደማይሆን እነሱን ከተኩት ከደርግ/ኢሰፓ ስርዓት ትምህርት ለመወስድ ያልቻሉ የአዕምሮ ስንኩላን ስብስብ መሆኑን ዳግም እያረጋገጡ ነው። እነሱ የተኩት ኢሰፓ ሁሉም የህብረተስብ  ክፍል ሁሉም ዜጋ  በግድ አባል ለማድረግ የሞከረ፣ በግለስብና በህዝብ ላይ ፍጹማዊ አገዛዝ (Totalitarian)  ለመዘርጋት ሞክሮ ያልተሳካለት፡ ለውድቀቱም አንዱ መንስኤ አሁን ወያኔ በማድረግ ላይ ያለውን በዜጎችና በህዝብ ላይ ፍላጎቱን በማስገደድ፤ በጉልበት መጫኑ ነበር። በኢሰፓ ርዕዮት አምነው ከልብም ተቀብለው ለፓርቲው ህልውና የታገሉና መስዋዕት የሆኑት ስንቶቹ እንደሆኑ በዚያች ቀውጢ ሰዓት የኢትዮጵያ ህዝብም ራሳቸው ወያኔዎችም የሚያውቁት ነው፡፡

ዜጎችን  በማስገደድ የስልጣናቸውን እድሜ ለማራዘም የስርዓቱ አገልጋይና የአፈና  መሳሪያ ለማድረግ የሚደረገው ይህ ሂደት የፋሽስቱን የወያኔን ስርዓት እድሜ የሚያራዝም አይሆንም። ታሪክ አንዳንዴ ራሱን ስለሚደግም የዚህንም ሂደት ውጤት የምናየው ይሆናል፡፡ ከወደቁ በኋላ መንፈራገጥ ለመላላጥ ከመሆን እንደማያልፍ ጥርጥር የለንም፡፡ በሚሊዮን የሚቆጠሩ የፓርቲ አባላት በሚሊዮን የሚቆጠሩ ሰላዮችና አፋኞች አምባገነናዊ ስርዓቶችን – ከሆስኒሙባርክ እስከ ሙአመር ጋዳፊ – ሊያድኗቸው እንዳልቻሉ  የቅርብ ጊዜ ምሳሌዎች ናቸው።

በስርዓቱ ውስጥ የሚገኙ ኢህአዴግ የሚባለው  የህወሃት መሳሪያ የሆነው ድርጅት አባላት አብዛኞቹ ለኑሮ ዋስትና፣ለእለት ጉርስ፣ የስራና የትምህርት እድል ለማግኘት ወዘተ ሲሉ አባል እንደሆኑ እናውቃለን። በኢትዮጵያዊነታቸው በዜግነታቸው ማግኘትና መጎናጸፍ የሚገባቸውን መብቶቻቸውን ለማግኘት ባለመቻላቸውና በመገደዳቸው እንደሆነ  ግልጽ ነው። ለሆዳቸው ሳይሆን ለህሊናቸው ጭምር ተጨንቆ ማሰቢያው ግዜው አሁን ነው፤ ጊዜው ሳይመሽ ከኢትዮጵያ ህዝብ ጋር መወገን እንላለን ።

ይህን ስርአት ከውስጡ እንዲታገሉት፤ የስርአቱ መናጆና ባይተዋር ለሆኑት ብዙሃኑ የኢሃአዴግ አባላት ጥሪያችንን እናቀርብላቸዋለን። የወያኔ ስርአት ዘረኛና ዘራፊ፤ የህዝብን መብቶች አፋኝ ስርዓት መሆኑን ከእነሱ በላይ እማኝ እንደሌለ ያውቁታል። ጥቂት ሺዎች የሚመዘብሯትና የሚንደላቀቁባት በአፈና በሽብር የሚገዟት ኢትዮጵያ እንደሆነች እነዚሁ ብዙሃን የኢህአዴግ አባላት ያዉቁታል። የፋሽስቱ ወያኔ ግብዓተ መሬት ሁሉንም ጠራርጎ ወደ ክፉኛ ወድቀትና አይቀሬው ግብዓተ መሬቱ ከመሄዱ በፊት ከህሊና  ጋር ተነጋግሮ ከአፋኞች፣ ገዳዮችና ዘራፊዎች ጋር አብሮ መቆም ሳይሆን በልዩ ልዩ መንገዶች የዚህን አሸባሪና የዘርኝነት ነቀርሳ የተጠናወተው ስርአት ወድቀት እንድታፋጥኑ፤ ከኢትዮጵያ ህዝብ ጋር እንድትቆሙ ጥሪ እናቀርባለን። በታሪክ ሆነ በህግም ፊት ከተጠያቂነት ለመዳን የሚቻለው ለዚህ ስርዓት እድሜ የማራዘም ተግባራትን በመፈጸም ሳይሆን የስርዓቱን እድሜ የሚያሳጥር ተግባራትን በማድረግ ብቻ ነው እንላለን።

የኢህአዴግ የሚባለው የህወሃት መጠቀሚያ ድርጅትም ሆነ የራሱ የፋሽስቱ የወያኔ ከፍተኛ ባለስልጣኖችና ከፍተኛ ጄነራሎች ዛሬ የዘረፉትን የህዝብ ገንዘብ በምዕራብ ሀገሮች ንብረት እየገዙበትና ወደ ውጭ ባንኮች ገንዘብ እያሸሹ እንደሆነ በየጊዜው የሚደርሱን በርካታ መረጃዎች አሉ። ቤተስቦቻቸውንም ወደ ውጭ የሚልኩ ጥቂቶች አይደሉም። እንድ እግራቸው አገር ውስጥ ሌላው ወደ ውጭ መሆኑን የኢትዮጵያ ህዝብም ሆነ ብዙሃኑ የስርአቱ ተከታዮችና ደጋፊዎች ሊያውቁት ይገባል።

የአፋኞችና የገዳዮች ምሽግ -የወያኔ ደህንነት

የፋሽስቱ አገዝዝ ያለፈውን የደርግ/ኢሰፓ መንግስትና በታሪክም  ያለፉትን የኢትዮጵያ አገዛዞችን ኢ-ፍትሃዊ፣ጨቋኝ፣ ሰው በላ፣ ወዘተ እያለ ሲከስ፣ ሲያወግዝ፣ ሲያሳጣ የነበረው ሰቆቃ ፈጻሚ ኢ-ሰብአዊ እያለ እንደነበር ሲታወስ፤ ዛሬ በኢትዮጵያ ታሪክ አቻ የማይገኝለት በሰብዓዊ ፍጡር ላይ ግፍ የሚሰራ፣ በኢትዮጵያውያን ዜጎች ላይ ሰቆቃ ፈጻሚ፣ አፋኝና ገዳይ ራሱ ወያኔ ህወሃት ነው::

ዛሬ ማዕከላዊ ምርመራ ሌሎችም የወያኔ የደህንነትና የፓሊስ ምርመራ ቦታዎች የምድር ሲኦል ሆነዋል። ሰው ከሰው መፈጠሩን የሚያማርርባቸው ስፍራዎች ናቸው። “ሞት ምርጫ ሆና ለሚሰቃዩት የማይቀርብበት” ከስቃይ ብዛት አዕምሮአቸውን የሚስቱበት ሲሆን፣ እጅግ ዘግናኝና አረመኔያዊ ሰቆቃዎች ሳቢያ በርካታ ኢትዮጵያውያን እዚያው በሰቆቃው ወቅት ህይወታቸው ያልፋል፤ ወንድ፣ ሴት፣ ሽማግሌ፣ ለጋ ወጣት ላይ ልዩነት አይደረግም፤ሁሉም ስቃይ ይቀበላል፤ በፍርድ ስም ይሸፈጣል። ዳኛው ከሰቆቃ ፈጻሚው ጋር አብሮ ንጹሁን ዜጋ ያጠቃል:: በወያኔ፤ ኢትዮጵያ ሰብዕናተዋርዷል፣ ሰብዓዊ ፍጡር ረክሷል:: የግፍ ጽዋ ሞልቶ ፈሷል!!

ዛሬ በየለቱ በማዕከላዊና በደህንነቱ መስራያ ቤት የአፈና ቪላ ቤቶች፣ በየክፍለ ሀገር እስር ቤቶች ለመስማት እንኳን የሚዘገንኑ ሰቆቃዎች በኢትዮጵያውያን ላይ ይፈጸማሉ። አካላቶቻቸው ይተለተላሉ፣ ይጎድላ፣ ይደማሉ፣ ይጮሃሉ። የትውልድ ብሄራቸው እየተጠቀሰ ይሰደባሉ፣ ሰብእናቸው በህወሃት መርማሪዎች ደጋግሞ ይዋረዳል፣ ፍርድቤት ሳይደርሱ ዓመታት ይማቅቃሉ፣ ለፍርድ ቤት ተብየው የወያኔ ቧልት ቢቀርቡም ባላመኑበት ባልሰጡት ቃል ይቀጣሉ።

ካፒቴን ተሾመ ተንኮሉ “ሞቶ መነሳት” በሚል ርዕስ የጻፈውን ብዙ ኢትዮጵያዊያን እንዳነበቡ እገምታለሁ። ይህንኑ አስመልክቶ በአየር ሃይል በተመደቡ የወያኔ ደህንነቶች ተወስዶ በጨለማ ቤት ተወርውሮ ለሁለት ዓመት ያህል  የደረሰበትን ስቃይና ግፍ አስመልክቶ ለኢሳትና ለሌሎች ሚዲያዎች የሰጠውን ቃለ ምልልስ ብዙ ኢትዮጵያውያን ተከታትለውታል የሚል እምነት አለኝ።

የወያኔ ታጣቂዎች በህዝባችን ላይ የሚፈጽሙትን ግድያ፣ ሰቆቃ፣ ግፍና፣ ዜጎችን የማዋረድ ተግባራት ከዜጎች አንደበት እጅግ ጥቂቱን ለማቅረብ እወዳለሁ። ጥቂቶቹን እንስማ፡-

  1. አቶ ጋስ – የአፋር ሰባዓዊ መብት በአፋር ውስጥ የስምንት ልጆች አባት የሆኑ ግለሰብ፣

  2. ድምጻችን ይሰማ የኢትዮጵያዊያን ሙስሊሞች በመብት እንቅስቃሴ ወቅት በቅርብ ሳምንት የወያኔ ፖሊሶችና ደህንነቶች ድብደባ፤ ስቃይና ውርደት ከደረሰባቸው ሴቶች አንዱዋ የምትለውን እንስማ፣
  3. https://www.youtube.com/watch?v=esqzanWRk0s&feature=youtu.be
  4. በራሱ በአቶ አንዳርጋቸው ላይ ወያኔዎች በተለመደ ጭካኔያቸው በምርጫ 97 ያደረሱበትን የጻፈውንና ጋዜጠኛ ሲሳይ አጌና በኢሳት ያቀረበውን በአጭሩ እናድምጥ፣
  5. በቅርብ ሳምንት ጠቅላይ ሚኒስቴር የሚባለው የፋሽስቱ የወያኔ አገልጋይ ለአንድ ሚዲያ ነኝ ለሚል ግለሰብ በሰጠው ቃለ ምልልስ እናድምጥይህን አሳዛኝ  ሰቆቃ በመአከላዊና በሌሎች ሰቆቃ መፈጸሚያ ቤቶች ወያኒዎች ዘግናኝና አሰቃቂ ሰቆቃ ከፈጸሙባቸው መካከል ለምሳሌነት ስለበደሎቻቸው ያልዋቸውን ደግሞ ቀጥሎ እንመልከት፡-“ዓይን ተሸፍኖ፣ እጅ በካቴና ታስሮ መደብደብ፣ ውስጥ እግርን ረፍ፣ የአውራጣት ጥፍር ማውለቅ፣ ቁስሉን መርገጥ፣ ጆሮን በጥፊ መምታት፤ አንዱ ፊት ሌላው ኋላ ሆኖ ጀርባንታፋንመቀመጫንወገብትከሻን መደብደብ። ደክም ግድግዳ አስደግፈው ብደብ፣ ስደክም በላውሃ እያፈሰሱ መደብደብ፤ ሰውነት ኪቆስል ድረስ መቀመጥ መነሳት ፤እስኪዝለፈለፍ ስፖርት መስራት፣ ሲያቅተው፣ ሲወድቅ መርገጥ፤መጫሚያ፣ ታፋን፣ የእጅ ጣቶችን፣ እራስን መቀጥቀጥ፤ የውስጥ ሱሬ ሳይቀር አስወልቀው ብልት መቀጥቀጥ፤ መሬት ሲዘረር አንገት ላይ በጫማ ቆሞ ማሰቃየት፤ ጡት ሳይቀር በኤለትሪክ ገመድ መግረፍ፤ ውስጥ እግር፣ መቀመጫ፣ ጀርባ መግረፍ፤ እጅ በካቴና አስረው በዚያ ግድግዳ ላይ መስቀል፤ በአካል ላይ ከፍተኛ ድብደባ፣ ለረጅም ሰዓት ዘቅዝቆ መሰቀል፣ ሲጮህ አፍ በጨርቅ መጠቅጠቅ፤ ክብር የሚነካ ስድብ፣ 45 ቀናት ማታ ማታ ድብደባ ለረጅም ሰዓት፤ አንድ ዓመት ከስድስት ወር ሲታሰር ፍርድ ቤት አልቀረበም፤ ለስድስት ወር እጅና እግሩ በእግር ብረት ማሰር፤ በድብደባ የግራ የዘር ፍሬው (ብልቱ) ሟሙቶ ጠፍቷል፤ በኤሌትሪክ ሰውነቱ ተጠብሷል፤ ለ48 ሰዓታት ምግብና ውሃ መከልከል፤  ለቀናት እንቅልፍ መከልከል፤  በአንድ እግር ለረጅም ሰዓታት ማስቆም” ።  በቅርብ ሳምንታት የሙስሊም ሴቶች ይህ ነው በማይባል ጭካኔና አረመኔያዊ መንገድ መገረፋቸው፣ልብሳቸው ወልቆ እርቃናቸውን እንዲሆኑ መደረጉ፣ የቁርዓን እና የመሳሰሉት እምነት ተኮር መገለጫዎች በታሰሩባቸው የፖሊስ ጣቢያዎች በሙሉ እንዲቃጠሉ ተደርገዋል።ሲለቀቁም እራቁታቸውን ሌሊት ሰው በማያያቸው ሰዓት ተፈትተው ወደሚሄዱበት እንዲሄዱ መደረጉ እውነታ ነው።ከላይ የተዘረዘሩን አሰቃቂ ጭካኔዊ ተግባራትን፣ ሰቆቃን፣ አፈናን ግድያን እንመራዋለን በሚሉት ህዝብ ላይ የሚፈጽሙ “ሰውን አንደበድብም፣ አናሰቃይም፣ አንገርፍም” በማለት እንደለመዱት ይክዳሉ።  ጠቅላይ ሚኒስቴር የሚባለው የፋሽስቱ የወያኔ አገልጋይ  ግለሰብ በሰጠው ቃለ ምልልስ፣ የወያኔው የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴርም በሌላ ቃለ ምልልስ የደገመው ይህንኑ አይናችንን ግንባር ያድርገው የሚል ክህደትና የተለምዶ ሽፍጦችን ነው።ከሶስት ሳምንታት በፊት በዋሽንግተን ዲሲ በአንዳንዶቹ የፋሽስቱ ወያኔ ሎሌዎችና ተላላኪዎች ላይ በተቆጡ ኢትዮጵያውያን ወጣቶች የደረሰባቸውን ማሸማቀቅ፣ ውግዘትና፣ ማስነወር “ብልግና” ተደረገ “ነውር” ተፈጸመ በማለት በዚያ ሰሞን እነሱና የስርዓቱ ተጠቃሚዎች በሆኑ ሚዲያዎች ያዙኝ ልቀቁኝ ሲሉ ተደምጠዋል። ሰዎች የሚከበሩት ሌላውን ሰው ሲያከብሩ፣ በጎ ሲሰሩ፣ መልካም ሲሰሩ፣ አርአያዊ ስነ ምግባር ሲኖራቸው ነው። ጨዋነት ያልተጻፈ ማህበራዊ ፕሮቶኮል ነው። የሚሰራው ጨዋዎች ባሉበት ማህበረስብ ሁሉ አብዛኛው ማህበረሰብ በጋራ የሚገዛበት የሚመራበት ማህበራዊ (Social Norm and etiquette ) ሲሆን ነው። ያለ መቀባበል (Reciprocity) ጨዋነት  የሚሰራ ሊሆን አይችልም።የወያኔ ጉዶች በአንጻሩ ምንም ሃፍረት ያልተፈጠረባቸው ይሉኝታና ሞራል የማያውቁ ኢትዮጵያና ህዝቡዋን ያዋረዱ፣ ቤተ ክርስትያንና መስጊዶችን ሳይቀር የሚያረክሱ ተግባራትን የሚፈጽሙ፣ ቅዱሳን መጽሃፍትን የሚያዋርዱ የሚያረክሱ፣የውንብድና የሽብር ተግባራት የሚፈጽሙ፣ በንጹሃን ዜጎች ላይ ሰቆቃ እየፈጸሙ የዜጎችን ቅስም መስበር ምንም የማይመስላቸው (Saddists) እጃቸው በደም ተጨማልቆ በጉልበት እየገዙ ያለምንም ይሉኛታ፤ በለየለት አይናአውጣነት ስለ ኢትዮጵያዊ ጨዋነት ሊሰብኩ ይዳዳቸዋል። የወያኔ ፋሽስቶችና ሎሌዎቻቸው በዘረኝነት፣ በዘረፋ፣ በአፈና ቅስም እየስበሩና እያዋረዱ፤ ፍርሃትን በህብረተስቡ ውስጥ  ስላነገሱ፣ በህዝብ እንዲከበሩ እንዲታፈሩ የሚከጅሉ የሌባ አይነ ደረቅ መልሶ ልብ አድርቅ የሚለው ብሂል ፈጽሞ የማይገልጻቸው እንደሆኑ በድጋሚ አረጋግጠውልናል።በዋሽንግተን ዲሲ ወጣት ታጋዮች እንደተደረገው በመላው አለም የወያኔ አገዛዝ መሪዎች የነሱ ሎሌ ባለስልጣኖቻቸው በተገኙበት ሀገር ከተማና ቦታ ሁሉ ማስነወር ማሸማቀቅ፤ ስላምና እረፍት መንሳት፣ የእግር ረመጥ መሆን በመላው ዓለም ተጠናክሮ መቀጠል ያለበት የትግላችን አካል ነው። ይህ ስልት የህዝባዊ እምቢተኝነት አካል ነው። የአልገዛም፣ አናከብርህም፣ አንቀበልህም፣ ወግድ የማለት የሰላማዊ አመጽ አካል ነው። በዴሞክራሲያዊ ሃገሮች በህግ የበላይነት ማቀፍ ውስጥ ለምንገኝ ሁሉ የመታገያ መሳሪያ በመሆኑ ይህን የትግል ስልት ተግባራዊ እንድናደርግ በመላው ዓለም ለሚገኙ ኢትዮጵያውያን ጥሪያችንን እናድሳለን ።እነዚህ ወደ ምእራብ ሀገሮች የሚመጡ  ባልስልጣኖቹም ሆኑ በእነሱ መሪነትና ውሳኔ ሰጪነት ባለፉት 23 ዓመታት በህዝብ ላይ ወንጀል የፈጸሙ፤ ስቆቃ፤ ግድያ፤ አፈና ጭካኔያዊ ተግባራትን በንጹሃን ዜጎች ላይ ያስፈጸሙና የፈጸሙ የደህንነት፣የፌደራል ፖሊስ፣ የልዩ ህይል፣ የክልል ፖሊስና በተዋረድ ያሉ የዚህ ስርአት የአፈና መዋቅሮች የወያኔ የስልጣን ምሰሶዎች በመሆናቸው በሁሉም መንገድ መታገልና ለፈጸሙት መጠነ ሰፊ ወንጀሎች በህግ ፊት እንዲቀርቡ ዝግጅቶችን ማድረግ ሌላው አንገብጋቢ የትግል ዘርፍ ነው።

    የወያኔ የብሄራዊ ደህንነት የሚባለው የአፋኞች፣ የሰቆቃ ፈጻሚዎችና፣ የገዳዮች ምሽግ በሚመለከት በደርግ ዘመን በደህንነትና በፓሊስ ውስጥ  ያገለግሉ የትግርኛ ተናጋሪዎች ተመርጠው እስካሁን በቁልፍ ቦታዎች ላይ እንደሚገኙበትማ እነማን እንደሆኑ እናውቃለን፤ ባዶ ስድስት በሚባለው የወያኔ እስር ቤት ጀምሮ ግፍ፣ ግድያና ሰቆቃ የፈጸሙ የወያኔ ህወሃት አባላት ፈላጭ ቆራጭ እንደሆኑበት በማእከላዊ ብቻ ሳይሆን በአዲስ አበባ በሚገኙ ሰቆቃ መፈጸሚያ ቪላ ቤቶች (Safe Houses) የት የት እንደሚገኙ፤ ምን ዓይነት ወንጀልች ሲፈጸሙ እንደነበር፤ በልዩ ልዩ የሀገራችን  አካባቢዎች ትግራይን ጨምሮ ተመሳሳይ ድብቅ የአፈና ቦታዎች በሺህ የሚቆጠሩ ዜጎችን የገደሉ፣ ያስገደሉ፣ ያሳፈኑ፣ ያፈኑ፤ ሰቆቃ የፈጸሙ እነማን እንደሆኑ  ንቅናቄያችን መረጃዎች አሉት።  በጎረቤት  ሀገሮች  በኬንያ፣ ጅቡቲ፣ ሱዳን፣ ደቡብ ሱዳን፣ እንዲሁም በቅርቡ የመን ድረስ ድንበር ዘለውና ባህር አቋርጠው ግድያ አፈና ያቀነባበሩ የፈጸሙት እነማን እንደሆኑ ከተለያዩ አቅጣጫዎች በርካታ መረጃዎች ለንቅናቄያችን እየደረሱ ናቸው።

    እነዚህን አፋኞችና ገዳዮች እንዲሁም ውሳኔ ሰጪ አለቆቻቸውን ለፍርድ ለማቅረብ የሚቻልበትን መንገዶች በመላው ዓለም የሚገኙ ኢትዮጵያዊያንና የህግ ባለሙያዎች ነዋሪ የሆኑባቸውን ሀገሮች  ህጎች በመፈተሽ ህጉ በሚፈቅደው መሰረት በኢትዮጵያ ውስጥ ለተፈጸሙ የጦር ወንጀሎች፣ የዘር ማጥፋት ወንጀል፣ የጅምላ ግድያ፣ ከፍርድ ቤት ውጭ የተደረጉ ግዳያዎች፣ አፈናዎች፣ ሰቆቃዎች ተጠያቂ የሚሆኑ የወያኔ ውሳኔ ሰጪዎች፣ ውሳኔ አስፈጻሚና ፈጻሚዎችን ፍርድ ፊት እንዲቀርቡ በተደራጀ መንገድ መንቀሳቀስ አንዱ የወቅቱ ዓብይ የትግል ተግባር ነው። በስዊድን የተጀመራውን የወያኔን ወንጀለኞች ወደ ፍርድ የማቅረብ ሂደት በሌሎችም የአውሮፓ ሀገሮች እንዲሁም በአሜሪካና በካናዳ መጀመር የትግሉ አንዱ ዘርፍ ነው።

    በኢትዮጵያ ውስጥ ቤተሰብ ዘመድ በወያኔ የታፈኑባችሁ፣ የደረሱበትን የማታውቁ፣ በወያኔ አፋኞች መገደላቸው ማስረጃ ያላችሁ፣ የደህንነትና የፖሊስ አፋኞች፣ ሰቆቃ ፈጻሚዎች፣ ገዳዮችን ማንነት መረጃዎችን የምታውቁ፣ ለዚሁ ተግባር ለሚቋቋሙ ግበረ ሀይሎች ስለወንጀለኞቹ ዝርዝር መረጃ በመሰብሰብ እንድትልኩ ጥሪ እናቀርባለን። ወንጀለኞች በተለይም በዴሞክራሲያዊ ምዕራብ ሀገሮች መሽሸጊያ እንዳያገኙ በውጭ ለምትገኙ ኢትዮጵያዊያን ሁሉ ስለእነዚህ ወንጀለኞች የምታገኙትን መረጃዎች ሁሉ እንድታቀብሉ ጥሪያችንን እናቀርባለን።

    ቀደም ሲል ፋሽስታዊው የወያኔ ዘረኛ  ስርአት ደካማና በቅራኔዎች ተቀስፎ የተያዘ ፤ ውስጡ የበሰበሰ፤ የነተበ ነው ብለናል። ካልገፋነው ግን ሊወድቅ አይችልም። እየተንፏቀቀና እየተንገዳገደ እንዳይቀጥል ገፍቶ መጣል ያስፈልጋል። ወያኔን በሥልጣን ላይ ያቆየውን የመከላከያና የስለላ ተቋማቱን ማዳከም አለብን። መስዋትነት ለመክፈል የተዘጋጁ ሃይሎችን መቀላቀል የሚችል ዜጋ ሁሉ እንዲቀላቀል ንቅናቄያችን ጥሪ ያቀርባል። በደጀን የተሰለፈው ኃይል ደግሞ የዘማቹን ስንቅ በማዘጋጀት በገንዘቡ፣ በጉልበቱ፣ በመረጃ ይተባበር። የተቆጣ፣ ጥቃት፣ ውርደት፣ ግፍ የመረረው ሁሉ ለነፃነቱ ግድ ያለው ኢትዮጵያዊ ሁሉ የስነ ልቦና ዝግጅት ያድርግ። ከወያኔ ሰላዮች ራሱን ተከላክሎ በያለበት በጥብቅ ከሚያምናቸው ጋር በመሆን በየአካባቢው በቡድን በቡድን ይደራጅ፤ የወያኔ ቀንደኛ ሹሞችና ወንጀለኞችን ይሰልል፤ መረጃዎችን ለንቅናቄችን በዘዴ እንዲልክ ጥሪ እናደርጋለን።

    በወያኔ ስር የሚገኘው የመከላከያ ሰራዊት

    ዘረኛውና እና ፋሽስቱ ወያኔ አርነት ትግራይ በኢትዮጵያዊያን ላይ የሚያደርሰው በደል፣ ግፍና ዘረኝነት ሌላው ገፈት ቀማሽ በፋሽስቱ ወያኔአባል በሆኑ የጦር መኮንኖች እዝና ቁጥጥር (Command and Control)  ተወጥሮ የተያዘው ከኢትዮጵያ ህዝብ አብራክ የወጣው ከአማራ፣ ከኦሮሞ፣ ከደቡብ ህዝቦች፣ ከአፋር፣ ከጋምቤላ፣ ከሌሎች ብሄር ቤሄረሰቦች የተመለመለው በታችኛው እርከን ላይ የሚገኘው ሰራዊት ነው።

    ይህ 5ኛና 6ኛ ክፍል ባልጨረሱ የወያኔ መኮንኖች ሙሉ በሙሉ በሚባል ደረጃ ተሰንጎ የተያዘ ሰራዊት ዘርፈ ብዙ በሆኑ ችግሮችና ቅራኔዎች እንደተወጠረ ከበቂ በላይ መረጃዎች አሉ። ኢትዮጵያ ስትዘረፍ፣ ወገኖቹ  ሲፈናቀሉ፣ ወንድምና እህቶችህ ሲሰደዱ ይህ ስራዊት የሚመለከት ነው።  ከላይ ከዋናው ኤታማጆር ጀምሮ ዕዞች፣ ክፍለ ጦሮች፣ ብርጌዶች፣ ሬጅመንቶች፣ ሻለቃ፣  ሻምበል እስከ ጋንታና እስከ ታች ጓድ ድረስ የፋሽስቱ ህወሃት አባላት በበላይነት የያዙት ይህን ያገጠጠ ዘረኝነት በየእለቱ የሚኖርበት በመሆኑ ሰራዊቱ ያውቀዋል። በችሎታ በአገልግሎትና በብቃት ሳይሆን በዘረኝነት የተጫኑበት እንደሆነ ይህ ሰራዊት በሚገባ ያውቃል። ይህ ሰራዊት ከስንቁ፣ ከአልባሳቱ፣ ከትጥቁ ጭምር እየዘረፉና እያጭበረበሩ በመነገድ እነዚህ የወያኔ አርነት ትግራይ አባላት በሆኑ አዛዦችና ጥቂት ተባባሪ ሎሌዎቻቸው እንዲከብሩም ያውቀዋል፡፡ 90 ከመቶ የሚደርሱት ከፍተኛዎቹ የህወሃት ጀነራሎች የዋና መምሪያ፣ የዕዝ፣ የልዩ ልዩ መምሪያዎች፣ የክፍለ ጦርና ከዚያም ዝቅ ብለው በተዋረድ የሚገኙ ቈልፍና ወሳኝ ቦታዎች ላይ በኃላፊነት የተቀመጡት የወታደራዊ ሳይንስ ትምህርት፣ እውቀት፣ የአመራር ብቃት፣ ልምድ ለ21ኛ ክፍለ ዘመን ዘመናዊ መደበኛ (የሽምቅ ተዋጊ ሃይል ያልሆነ ማለት ነው) ሰራዊት  እዝና ቁጥጥር (Command and Control) በምንም መለኪያ የማይመጥኑ ምናልባትም ለዚህ እጅግ አሳፋሪ ሁኔታ ኢትዮጵያ ብቸኛዋ ሀገር እንድሆነች ከታች ያለው ከታች የሚገኘው ብዙሃኑ የመከላከያ ሰራዊቱ አባላት ሊገነዘቡ ይገባል።

    የፋሽስቱ ወያኔ ታማኝ ጀነራል መኮንኖች አብዛኞቹ ነጋዴዎች፤ ሙሰኞች፤ ዘራፊዎች እንደሆኑ፤ ባለብዙ ፎቅ ህንጻዎች ባለንብረቶች እንደሆኑ፤ ልዩ ልዩ ሃብቶችን እንዳጋበሱ፤ ወደ ወጭ ሀገሮችም ገንዘብ እንደሚያሸሹ፤ ቤተስቦቻቸውንም እንደሚያሸሹ ይህ ሰራዊት በሚገባ ያውቀዋል። በአንጻሩ የተበላሸ ስንቅ እየመገቡት፤ በሰበብ  አስባቡደሞዙን እየቆረጡ በችግር ይቀጡታል። የደሞዝ፣ የአልባሳት፣ የምግብ አስከፊ ሁኔታዎችን አስመልክቶ ጥያቄ  ያነሱ የጦሩ አባላት ከልዩ ልዩ ግንባሮች ታፍነው የጠፉ፤ እስከአሁንም ድረስ የደረሱበት እንደማይታወቅ ሰራዊቱ  ስለሚኖርበት የሚታዘበው፤ በልዩ ልዩ ወቅቶች ሰራዊቱን እየጣሉ የኮበለሉ የስራዊቱ መኮንኖች፣ የበታች ሹሞችና ወታደሮች  በይፋ እንዳጋለጡ ይሰማል፤ እርሱም በየግንባሩ ይሰማል።  በግምገማና በልዩ ልዩ ስልቶች  እርስ በእርሱ እምነት እንዳይኖር፣በጥርጣሬ እንዲተያይ፣  ለአንድ ሰራዊት የውጊያ ብቃት ወሳኝ ከሆኑት መስፈርቶች አንዱ የጋራ የውጊያ መንፈስ (Esprit de corps) የሌለው መሆኑን እናውቃለን፡፡ እርስ በእርስ መተማንን (Cohesion) እንዳይኖረው፤ በፖለቲካና በብሄር ተከፋፍሎ ተንፈራቆ እንዲቆም፣ የጎሪጥ እንዲተያይ፣ በራሱም እንዳይተማመን የተደረገ በዚህም ምክንያት ሞራሉ እንዲላሽቅ መደረጉ የሚኖርበት ሃቅ መሆኑን የታችኛው የመከላከያ ስራዊት አባላት ያውቁታል እየኖሩበትም ነው።

    ወያኔ ጦርነት ባወጀ ቁጥር፤ ጠብ በጫረባቸው ወቅቶች ሁሉ  መቶ በመቶ ከፊት እንዲጋፈጥ፤ የጥይት እራት እንዲሆን፤ፈንጂ ረጋጭ የሚያደርጉዋቸው የኦሮሞ፣ የአማራ፣ የደቡብ የጋምቤላ እንዲሁም የሌሎች ብሄር ብሄረስብ አባላትን እንጂ በዘረኝት በላዩ ላይ በአዛዥነት የተጫኑበት የወያኔ አርነት ትግራይ ወታደራዊ ሹሞች እንዳልሁኑ ያውቃል፤ ኖሮበታልም። በ 1990 –1992 (እ.ኤ.አ. 1998-2000) ከኤርትራ ጋር ወያኔ ባደረገው ጦርነት በሺዎች የሚቆጠሩ ለጋ ወጣት ወንድሞቹን ፈንጂ ረጋጭ አድርገው ለእልቂት እንደዳርጉዋቸው ያውቀዋል። በመጨረሻው በ2000 ዓ.ም. በተደረገው ውጊያ የጦርነቱን ሁኔታ ለመለወጥ የተቻለው በወታደራዊ ሳይንስ በልምድ በብቃት ምርጥና ከፍተኛ ዝና የነበራቸውን ብ/ጄነራል ተስፋይ ሀብተማርያም አየር ወለድ (ከብ/ጄነራል ለገሰ ተፈራ ጋር የህብረተሰባዊት ኢትዮጵያ የላቀ ጀግና ሜዳልያ ተሸላሚ)  ብ/ጄነራል በሀይሉ ክንዴ ታንከኛ፣ ብ/ጄነራል ንጉሴ አዱኛ መድፈኛ፣ ብ/ጄነራል ተጫኔ መስፍን ከአየር ሃይል፣ እንዲሁም በብዙ ሺህ የሚቆጠሩ በደርግ ኢሰፓ ስር በነበረው የቀድሞ የኢትዮጵያ ሰራዊት ውስጥ ያገለገሉ ወያኔ ከደርግ ውድቀት በኋላ እነሱና ቤተሰቦቻቸውን ለውርደትና ለችግር የዳረጋቸው የቀድሞ ሰራዊት የመስመር መኮንኖች፤ ባለሌላ ማዕረግተኞችና ወታደሮችን መልሶ በማስገባት ነበር። ከተጠቀሙባቸው በኋላም መልሰው ነው ያባረሯቸው። ይህን የዘረኝነት በቀጽሞ ሰራዊት አባላት ላይ የተፈጸመ ዳግመኛ የግፍ  ታሪክ ብዙው የኢትዮጵያ ህዝብ አያውቀውም። ወያኔዎች በእነዚህ ሙያዊ ብቃትና ክፍተኛ አስተዋጽዖ የጦርነቱን ሁኔታ ለመለወጥ መቻላቸውን ህዝብ እንዲያውቅ ማድረግ ዘረኝነታቸውና የበታችነት ስሜታችው  አልፈቀደምና። እ.ኤ.አ. በ2006 ወያኔ ሶማሊያን ሲወርር ማን ከፊት ሆነው እንደተማገዱ ፈንጂ ረጋጮች እነማን እንደነበሩ ይህ ሰራዊት አይቶአል፤ ያውቀዋል። ኖሮበታል።

    በወታደራዊ ሳይንስ ትምህርታቸው በአለም ታዋቂ ከሆኑ የጦር ኮሌጆች፣ ወታደራዊ አካዳሚዎች፣ ስታፍና ኮማንድ ተቋማት የተመረቁ የምድር ፣ የአየርና የባህር ምርጥ የበላይ አዛዦችና የመስመር መኮንንኖች በብዛት ነበሩበት።  የሶማሊያ ወራሪን ጦር ሃይል መክቶ ከማባረር እስከ ሰሜን የጦር ግንባሮችን ይህ ነው በማይባል ጀግንነት የተዋጋ  ሰራዊት የነበረበት።  ይህ ግምሽ ሚሊዮን የሚገመትና ከአፍሪካ ውስጥ ከነበሩት የመከላከያ ሰራዊቶች ትልቅ ከሚባሉት ፤ እስከ አፍጢሙ በዘመናዊ መሳሪያዎች ታጥቆ የነበረው በደርግ ኢስፓ አመራር ስር የነበው የኢትዮጵያ የመከላከያ ሰራዊት ውድቀት በዋነኝነት የሚቀርቡት ምክንያቶች ለ23 ዓመታት ወያኔዎች ህዝብን ለማንበርከክና አይበገሬዎች ነን የሚል የውሸት ታሪክ ለመጻፍ እንደሞከሩት፣ እንደሚፎክሩት አይደለም። ወያኔዎች   ከሌላው ኢትዮጵያዊ የተለየ ጀግንነት የወያኔዎች የወታደራዊ ብቃትና ስትራቴጄካዊ ብስለትና እወቅት ስለነበራቸው ሳይሆን  የኢትዮጵያ ህዝብና  በወቅቱ የነበረው የደርግ/ኢሰፓ መንግስት ሆድና ጀርባ ስለነበሩ ነው። የነበረው አገዛዝ  ፖሊሲዎችና ብዙዎቹ ተግባራቱ የህዝብን ልብ ስላሸፈቱ፤ ቅራኒዎቹም  የህዝብ ድጋፍ ስላሳጡት፤ ስራዊቱም የህዝቡ ነጸብራቅ ስለነበረ በዘርፈ ብዙ ቅራኔዎች ሰለባ ሰለተደረገ እንደነበር  የዛሬው የመከላከያ ሰራዊት ከዚህ ከራሱ ታሪክና ከሌሎችም ሃገራት የወታደራዊ ውድቀት ታሪኮች ማወቅ ይገባዋል።

    ዘመናዊ መሳሪያ እስከአፍንጫ ቢታጠቅ ፤ ሰራዊቱን በሚሊዮን ቢያደራጅ፤ ስርዓቱ በህዝብ የተተፋ፤ በቅራኒዎች የተዋጠ–በተለይም እንደወያኔ ዘረኛና ዘራፊ አገዛዝ፤ ሀገራዊ ራእይ ባላቸው ግፍና በደል አንገሽግሾዋቸው ፍትህና ነጻነት የተራቡና የተጠሙ የህይወት መስዋትነት ለመክፈል በቆረጡ፤ የህዝብ ልጆችና በኢትዮጵያ ህዝብ ደጀንነት በአቸናፊነት እንደሚጠናቀቅ ከአገራችንም ሆነ ከሌሎች አምባገነናዊ ስርዓቶች ውድቀት መማር የግድ ነው።  ከላይ እንደገለጽነው ህገ መንግስታዊ ስርዓቱን ለመጠበቅ የሚለው የሰራዊቱ ዓላማ በራሱ በወያኔ የተደፈረ፤ የተረገጠ ህገ መንግስት በመሆኑ  የሞተ ሰነድ ባዶና ቀፎ በመሆኑ ህይወቱን የሚገብርበት ምክንያት የዛሬው የመከላከያ ሰራዊት ሊኖረው አይችልም። የሁሉም ብሄረሰቦች እኩልነትና የተመጣጠነ ሰራዊት በሚል የተቀመጠውም የወያኔዎች ቡዋልት ከመሆን ያላለፈ መጭበርበሪያ እንጂ ዛሬ ይህ ስራዊት በአንድ ብሄር በአንድ ቋንቋ የበላይነት በፋስሽቱ የወያኔ አርነት ትግራይ ጀነራሎችና መኮንኖች  ፈላጭ ቆራጭነት ከላይ እስከ ታች ስር እንዳለ ከታች ያለው የመከላከያ  ሰራዊት ያውቀዋል። በወያኔ ስር የሚገኘውን የመከላከያ ሰራዊት ዘርፈ ብዙ ችግሮችና ቅራኔዎች እንዲሁም ደካማነት በሚመለከት በወታደራዊ ሳይንስ የላቀ እውቀት፤ ልምድና በህወአት ስር ስለሚገኘው የመከላከያ ሰራዊት  ወቅታዊ መረጃ ባላቸው የአየርና የምድር መኮንኖች የተደረጉ ጥናቶችን ንቅናቄያችን በቅርቡ ይፋ ያደርጋል።

    የፋሽስቱ የወያኔ አርነት ትግራይ ጀነራሎችና ወታደራዊ መኮንኖች እንደ ሲቪል የወያኔ ዘመዶቻቸው፤ በጎሬጥ የሚተያዩ፣ የሚናናቁ፣ በጥቅምና በስልጣን የሚሻኮቱ፤ የተቋሰሉ እንደሆነ ከታች ያለው ሰራዊት ያውቀዋል። አንዳንዶቹ ልባቸው የሸፈተና አጋጣሚና ጊዜ ቢያገኙ እርምጃ ለመውሰድ የሚያደቡ እንዳሉ በልዩ ልዩ ጊዜዎች ንቅናቄችን መረጃዎች ደርሰውታል። በ3ኛ ሀገሮች ከንቅናቄው ተወካዮች ጋር ለመገናኘት መልዕክት የላኩም አሉባቸው። አላማቸው፣ ራዕይያቸውና ግባቸው ህዝባዊ ስላልሆነ በንቅናቄው በኩል የእነዚህ የህወሀት መኮንንኖች ጥያቄ ተቀባይነት አላገኘም።

    በዘራፊ፣ ሙሰኛና ዘረኛ የወያኔ ወታደራዊ አዛዦች ለሚመራው ከህዝብ አባራክ ለወጣው ሰራዊት የምናቀርብለት ጥሬ መሣሪያውን በግፈኞችና በፋሽስቶች ላይ እንዲያዞር ነው። የነፃነት ታጋዮችን እንዲቀላቀል ጥሪ እናደርጋለን። ነገ ጥለውትና አጋልጠውት ለሚፈረጥጡ የዚህ የዘረኛና ዘራፊ ስርዓት ግፈኛ መሪዎች መሳሪያ ሳይሆን የህዝብ ወገን መሆን መርጦ ራሱን ኢትዮጵያንም፤ ከአብራኩ የወጣበትን የኢትዮጵያ ህዝብ ከውርደት እንዲያወጣ ንቅናቄያችን ጥሪ ያቀርብለታል!

    የተከበራችሁ ኢትዮጵያዊያን ፦ይህን ትግል ዳር ለማድረስና  በድል ለማጠናቀቅ ዋና መሰረቱ ጠንካራ ድርጅት ነው።

    • ግንቦት 7፣ የኢትዮጵያን ሕዝብ አስተባብሮ ወደ ድል ለመምራት ዝግጁ ነው፤ ድርጅታዊ አቅሙን እንድናጠናክር ለሁሉም አትዮጵያዊ ጥሪ እናደርጋለን፤
    • ግንቦት 7 ሁለገብ ትግልን – ሕዝባዊ ተቃውሞን፣ ሕዝባዊ እምቢተኝነትን እና ሕዝባዊ አመጽን – አስተባብሮ መምራት ወደሚችልበት ደረጃ ለማድረስ በጋራ ቆርጠን እንድነሳ ጥሪ እናደርጋለን፤
    • ትግሉ ኢትዮጵያ ውስጥ፣ በአጎራባች አገሮችና ኢትዮጵያዊያን በሚኖሩባቸው ሌሎች አገራት ውስጥ በመሆኑ በሁሉም ቦታዎች ድርጅቱን በማስፋት እንድናጠናክር ጥሪያችንን እናቅርባለን፤
    • ትግሉ በከተማም በገጠርም፤ በአገር ውስጥም ከአገር ውጭም በመሆኑ እነዚህን  አስተባብሮ  የሚመራ ድርጅት ያስፈልጋል።

    በፀረ-ወያኔ ካምፕ ውስጥ የሚገኙ የፓለቲካ ድርጅቶች የሚዋሃዱበትና የሚቀናጁበት ወቅት አሁን ነው። ከሁሉም በላይ ከወያኔ በኋላ የተዋሃደችና የጠነከረች ኢትዮጵያ እንድትኖረን ካሁኑ አገር አድን ኃይል ማደራጀት አስፈላጊነቱን ንቅናቄያችን ከምንም በላይ ይገነዘባል። በዚህም መሠረት ግንቦት 7 በተግባራዊ ትግል ውስጥ ካሉ ድርጅቶች ጋር በየጊዜው እየዳበረ መጥቶ የአገር አድን ኃይል ምሥረታን ያለሙ ኅብረቶችን ለመፍጠር ጥረት ሲያደርግ ቆይቷል። በዚህም መሠረት:

    በዓላማ፣ በአደረጃጀትና በስልት ከሚመስሉን ለመዋሃድ ጥረት እናደርጋለን። በአሁኑ ሰዓት ከኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባር እና ከአማራ ዲሞክራሲያዊ ኃይሎች ንቅናቄ ጋር

    ለመዋሀድ ተስማምተን እየሰራን እንገኛለን። በዓላማ የምንስማማ ሆኖ አደረጃጀታችንን የማቀራረብ ሥራ የሚጠይቅ በሚሆንበት ጊዜ በጥምረት ለመሥራት ጥረት እናደርጋለን። በዚህ ረገድ የሚጠቀሱት  ከትግራይ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ (ትሕዴን)፣ በጄኔራል ከማል ገልቹ የሚመራው ኦነግ እና ከአፋር ሕዝብ ፓርቲ ጋር የመሠረትናቸው ጥምረቶች  አብይ ምሳሌ  ናቸው። በተለይ ከትሕዴን (ደሚት) ጋር የምንሠራቸው የጋራ ሥራዎች እየጎለበቱ መጥተዋል። ከሌሎች የኢትዮጵያ ድርጅቶች ጋር ለጋራ ሥራ የምናደርጋቸው ትብብሮች፣ በዚህ ረገድ የሚጠቀሱት የቤኒንሻጉል ሕዝቦች ንቅናቄ፣ የጋምቤላ ሕዝቦች ንቅናቄ፣ ኦነግ፣ አብነግ በአርአያነት ይጠቀሳሉ።

    ዛሬ ለሁሉም ለነፃነቱ፣ ለሰብዓዊ ክብሩና መብቶች ለሚቆረቆሩ ኢትዮጵያዊያን  የቀረቡትአማራጮች ሁለት ብቻ ናቸው።

    • በዜጎች ላይ ጭካኔዎች የሚፈጸሙባት፤ የሰው ልጆች ሰብዓዊ ፍጡራን ለአርመኔያዊ ግፍና ስቆቃ በሚዳረጉባት ሀገር፤ በውርደትና በደል የሚማቅቁባት፤ ዘራፊና ዘረኛጥቂት ፋሽስቶች  እንዳሻቸው የሚፈነጩባት፣ ብዙሃኑ ኢትዮጵያዊ ባይተዋርና የበይ ተመልካች፣ መብትና ሀገር አልባ የሆነ በሶስተኛ ዜግነት፤ እንዲያውም በባርነት አንድ ጊዜ ብቻ የሚኖርበት፣ የምትኖርበት በዚህ አለም  ውድ ህይወቱን በሲኦል የሚገፋበት አንዱ አማራጭ ነው፡፡
    • በሌላና በተጻጻሪው የሚገኘው አማራጭ ደግሞ የሰው ልጅ፤ ሰብዓዊ ፍጡር፣ ማንም ኢትዮጵዊ ዜጋ ምንም ያድርግ ወይም ታድርግ ወንጀል ቢፈጽም እንኳን በህግ የበላይነት — በግፍ ሰቆቃና ቅስም ሳይሰብር፣ ውርደት ጭካኔያዊ ተግባራት ሳይፈጸምበት– ቅጣቱን የሚቀበልበት የህግ የበላይነትና ነጻ ዳኝነት የነገሠባት ኢትዮጵያ ናት። እያንዳንዱ ዜጋ፣ እያንዳንዱ ብሄር ብሄረሰብ አሮሞው፣ አማራው፣ የደቡብ ህዝቦች፣አፋሩ፣ ኦጋዴኑ፣ ጋምቤላው፣ ህይወታቸው፤ እድላቸው  በእንደአሁኑ በጥቂት ዘረኞችና በእነሱ ሎሌዎች ሞግዜትነት፤ ፈላጭ ቆራጭነት የሚወሰንበት፣ በላያቸው  ላይ የሚሾሙበት፣ በግድ የሚጫኑበት ሳይሆን ብሄር፤ ብሄረሰቦች ፤ እያንዳንዱ ህዝብ በየአካባቢው ነጻና ርዕታዊ በሆነ ዲሞክራሲያዊ መንገድ ራሱ በሚመርጧቸው መሪዎች/ተወካዮች  ብቻ የሚተዳደርበት ስርዓት በትግላችን እወን ማድረግ ብቸኛው አማራጭ ነው፡፡
    • ምርጫችን ሙስሊም ክርስቲያን ኢትዮጵያውያን፣ ሁሉም የእምነትቶች፣ መብቶቻቸው የሚረጋገጥበት፤ ስብዕናቸው፣ ድምጻቸው የሚከበርበት፣ እምነቶቻቸው በሚፈቅዱት መስረት የራሳቸውን ጉዳዮች በራሳቸው መንገድ በነጻ የሚወስኑበት፣ በመንግስት ጣልቃ ገብነት ሳይሆን በህግ የበላይነት ብቻ የሚወስኑበት፣ በምንም መልኩ የማይደፈሩበት፣ የማይዋረዱባት፣ የማይረገጡባት፣ የኢትዮጵያ ሴቶች ለስደት ባርነት ተዳርገው ለስቃይ ለበደል፣ ለወርደትና ጥቃት በየአረብ አገሩ የማይሸጡባት ኢትዮጵያ በትግላችን እውን ማድረገ ብቸኛው አማራጭ ነው።
    • ምርጫችን ስልጣን የተገደበባት፣ አንዱ ስልጣን ሌላውን ስልጣን የሚቆጣጠርባት፣ ስልጣን ህዝብን ማገልገያ እንጂ ለመንግስታዊ ዘረፋ የማይውልበት፣ ህዝብን ለማገልገል እንዲ ህዝብን መገልገያ የማይደረግበት፣ ስልጣንና ባለስልጣናት ለህዝብ ተጠያቂ የሚሆኑባት፣ ትክክለኛ የህዝብ ወሳኝነት ዴሞክራሲያዊ ስርዓት የሚረጋገጥበት ፤ ሰብዓዊት የሰፈነባት ፤ የዜጎችዋ ሰቆቃና ስቃይ፣ ወርደትና ስደት፣ ድቀት የሚያከትምባት፣የነጻነት አየርን ሁሉም ዜጎች የሚተነፍሱባት፣ ትክክለኛ ዴሞክራሲያዊ የፖለቲካ ስርዓት የነገስባት ኢትዩጵያን በትግላችንና በሁለንተናዊ በመስዋእትነት እውን ማድረግ የቀረበልን ብቸኛ አማራጭ ነው።
    • ምርጫዎችን የመወስን ወስኖም ለተግባራዊ የትግል እንቅስቃሴዎች ዝግጁ መሆን ጊዜው አሁን ነው!! ንቅናቂያችን ለኢትዮጵያ ወጣቶች፤ የዩኒቨርሲቲና የከፍተኛ ሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎች፣ ለሁሉም ብሄር ብሔረሰቦች፣ የልዩ ልዩ እምነት ተክታዮች፣ ለኢትዮጵያ ሴቶች አልገዛም ባይነት፣ የህዝብ እምቢተነት፣እንዲሁም አመጽ እንዲያቀጣጥሉ ንቅናቂያችን ጥሪውን ያቀርባል!! የመንግስት ሰራተኞች ስራ በመጎተት ስራ በማቀዝቅ ስርዓቱን የበለጠ እንዲያዳክሙት ጥሪያችንን እናቀባለን።

    የተዋበች፣ ሰብዓዊትነት የሰፈንባት፣ የገዢዎ ሳይሆን፣ የዘረኞች ሳይሆን የህግ የበላይነት ብቻ የነገሱባት የሁሉም ብሄር ብሄረሰቦች እኩልነት ፍትሃዊ የሆነ የሃብት፣ የስልጣን፣ የጥቅም ክፍፍል የሚረጋገጥባት ፤ የእያንዳዱ ዜጋ ነጻነት የተረጋገጠባት ዴሞክራሲያዊት ኢትዮጵያን  በትግላችን በመስዋዕትነት እውን ለማድረግ ሁላችንም ቆርጠን እንነሳ! የምንችለውን አይነት መስዋዕትነት በእጥፍ ድርብ ለመክፈል በጋራ ተነስተናል!! ሁሉም የሚችለውን የትግል ዘርፍ መርጠን ያለውን ጠጠር ሁሉ እንወረውራለን!! ለዚህም ቃል ኪዳን እንገባለን።

    አትላንታ ፤ ኦገስት 31፡ 2014

    Etfreedom.2015@gmail.com

PDF  -- http://www.zehabesha.com/amharic/wp-content/uploads/2014/09/በወያኔ_ስር_የሚገኘው_የመከላከያ_ሰራዊትፍይናል.pdf”]

በመጨረሻ… ለጋዜጠኛ ዳርዮስ ሞዲ ህክምና መቶ ሺህ ብር ተሰጠ!

$
0
0
ዳርዮስ-ሞዲ

ዳርዮስ-Sep 6,2014

ኢ.ኤም.ኤፍ) አንድ ትውልድ ወደኋላ ከተሻገርን ጋዜጠኛ ዳርዮስ ሞዲን የማያውቀው የለም። በተለይም እ.ኢ.አ ግንቦት 13 ቀን፣ 1983 ዓ.ም. የወቅቱ የአገሪቱ ፕሬዘዳንት፤ ኮ/ል መንግስቱ ኃይለማርያም አገር ለቀው ሲወጡ ዜናውን ያነበበው ጋዜጠኛ ዳርዮስ ሞዲ ነበር። በሳምንቱ ኢህአዴግ አገሪቱን ከተቆጣጠረ በኋላ… የጠመንጃ አፈ ሙዝ ግዳጅ ተጨምሮበትም ቢሆን ዜናዎች ያነብ እንደነበር ብዙዎች ያስታውሳሉ። ይህ እውቅ ጋዜጠኛ በህመም ላይ መሆኑ ከተነገረ ሰነበተ። ሆኖም የሰራበት ማስታወቂያ ሚንስትር መስሪያ ቤትም ሆነ ሌሎች በተፈለገው አቅም ሊደርሱለት አልቻሉም።

ከጋዜጠኞች አለምነህ ዋሴ በግሉ ያደረገው ጥረት እንዳለ ሆኖ ሌሎች የነጻ ፕሬስ ውጤቶች የዳርዮስ ሞዲን ህይወት ለመታደግ የየራሳቸውን ድርሻ ሲያበረክቱ ቆይተዋል። ሆኖም የሚፈለገውን ያህል ገንዘብ አልተገኘም ነበር። ትላንት ምሽት ላይ የሰማነው ዜና ግን ከሌላው ግዜ የተለየ እና “እፎይ” የሚያስብል ነው። አንጋፋው የኢትዮጵያ መድህን ድርጅት ለጋዜጠኛ ዳርዮስ ሞዲ ህክምና የአንድ መቶ ሺ ብር እርዳታ ሰጥቷል። (በነገርዎ ላይ መድን ድርጅት በሚጠናቀቀው የኢትዮጵያ አመት፤ ለደንበኞቹ የ3 ትሪሊዮን የኢትዮጵያ ብር የመድህን ዋስትና ሸጧል። ይህም በታሪክ የመጀመሪያው ከፍተኛ ገንዘብ ነው።)

የጋዜጠኛ ዳርዮስ ሞዲ የቅርብ ሰዎች እንዳሉት ከሆነ፤ ይህ ገንዘብ ቀሪውን ህክምና እንዲያደርግ የሚረዳው ነው። መድህን ድርጅት እናመሰግናለን… ብለዋል። ጋዜጠኛ ዳርዮስ ሞዲም ምስጋና ያቀረበ መሆኑ ተያይዞ ተገልጿል። እንግዲህ ይንን መልካም ዜና ይዘን፤ ባለፈው ወር አዲስ ጉዳይ መጽሄት ሃምሌ 26/2006፤ በጋዜጠኛ እንዳለ ተሺ አማካኝነት ከዳርዮስ ሞዲ ጋር የተደረገውን ቃለ ምልልስ ልንጋብዛቹህ ወደድን። እንዲያው ጋዜጠኛ ዳርዮስ ሞዲን እንድናስታውሰው ያህል ነው ቃለ ምልልሱን ያቀረብንላቹህ።

በጋዜጠኝነት ከ30 አመታት በላይ በብስራተ ወንጌልና በኢትዮጲያ ሬዲዮ ሰርቷል። በወቅቱ የነበሩ የሬዲዮ አድማጮች በተለየ የዜና አቀራረቡና ድምጹ ይለዩታል። በሰራባቸው አመታት ተደብድቧል፥ ታስሯል ከስራ መታገድ ሁሉ ደርሶበታል። ግና ይህን ሁሉ መስዋእትነት የከፈለበት ተቋም ዛሬ ላይ የአልጋ ቁራኛ በሆነበት ሁኔታ ከጎኑ ሊቆም አልወደደም፥ የጋዜጠኛውንም ችግር ለህዝብ ማሳወቅ የፈለገ አይመስልም፡፡ ይህ ሰው በአሁኑ ወቅት በከፍተኛ የልብ ህመም እየተሰቃየ ይገኛል፡፡ ጋዜጠኛ ዳርዮስ ሞዲ ነው፡፡ ከዚህ የዘመን ባለውለታ ከሆነው ጋዜጠኛ ዳርዮስ ሞዲ ጋር በተክለሃይማኖት ጠቅላላ ሆስፒታል ለአንድ ሰአት ያህል ቆይተናል። ጋዜጠኛ ዳርዮስ ሞዲም ከህመሙ ጋር እየታገለ ቅን አንደበቱን አልነፈገንም፡፡ እነሆ ቆይታውን፡-


– ህመሙ የጀመረህ መቼ ነው?
* በአጠቃላይ አንድ አመት ከሶስት ወራት ተቆጥሯል።
– በእነዚህ ጊዜያት ውስጥ የት የት ህክምናህን ተከታተልክ?
* በመጀመሪያ በጳውሎስ ሆስፒታል ለአንድ ወር ያህል ታከምኩ። እንደገና በሽታው ሲያገረሽብኝ በአንድ የግል ሆስፒታል ተመላልሼ ከታከምኩኝ በኋላ ተሽሎኝ ለተወሰነ ጊዜ እንቅስቃሴ ሳደርግ፥ እንደገና አገርሽቶብኝ የካቲት 12 ሆስፒታል ህክምና ለማግኘት ስሄድ፥ አገልግሎት ሊሰጡኝ ፈቃደኛ ሳይሆኑ ሲቀር ቀጥታ አሁን ወዳለሁበት ሆስፒታል አርብ ሐምሌ 18 ቀን 2006 አ.ም ሕክምናዬን መከታተል ጀመርኩ።
– ለአንድ አመት ከሶስት ወር ያህል ስትታመም ከጎንህ ማን ነበር?
* ቤተሰቦቼ፥ የሚያውቁኝ ሰዎችና ጓደኞቼ አብረውኝ ናቸው።
– የእድሜህን ግማሽ ያህል የሰራኸው ማስታወቂያ ሚኒስቴር ይመስለኛል፡ ይህ ድርጅት በአሁን ሰአት በአንድ የአለም ዋንጫ እስከ 30ሚልየን ብር ገቢ እያስገባ፥ አንተን ለመርዳት ወይም ያለብህን ችግር ለሕዝብ ይፋ ለማድረግ ያልፈለገው ለምን ይመስልሃል?
* በጣም አስቸጋሪ ጥያቄ ነው። እንኳን መርዳት መኖሬን የሚያውቁ አይመስለኝም። እባክህ በዚህ ዙሪያ የምታነሳው ጥያቄ ካለ ቢበቃ ይሻላል።
– አንድ ሰው አቅሙ እስከፈቀደ ድረስ አንድን ተቋም አገልግሎ፥ አሁን አንተ እንደደረሰብህ አይነት ሕመም ሲገጥመው ያ ተቋም ከጎኑ ቆሞ አለሁልህ ካላለው፥ ሌላውን በዚህ ስራ ውስጥ እንዲያልፍ ለመምከር ያበረታታል?
* ይሄም ሌላኛው አስቸጋሪ ጥያቄ ነው። አንዳንዶች ለተወሰነ ጊዜ በጋዜጠኝነት ሙያ ያገለግሉና ቀንቷቸው የስኬትን ቁልፍ የሚጨብጡ አሉ። እንደ እኔ አይነቱ ደግሞ ሌሎች መውጫ በሮችን መመልከት ባለመፈለግ ብቻ፥ ስጋውን የሚያስደስትበት ገንዘብ ሳያገኝ እድሜው ገፍቶ፥ በችግር ተጠልፎ የሚወድቅበትን ይመርጣል። ብቻ ዋናው ነገር እከሌ በዚህ ቢያልፍ ጥሩ ነው፥ አይደለም የሚለውን ሁሉም በግሉ ቢያየው እመርጣለሁ።
– ያንተ ስሜት ግን ምንድነው የሚነግረን?
* ይሄን ያህል አመት ለማስታወቂያ ሚኒስትር በማገልገሌ የተሰማኝ ነገር የለም። ቁጭትና ሐዘን የሚሰማኝ በግሌ ነው፡፡ ከእኔ ጋር ይሰሩ የነበሩ ሰዎች የት እንደደረሱና ምን እንደያዙ አውቃለሁ። ግን ለምን እዚህ ቦታ ደረሱ፥ ለምን ይሄን አገኙ ብዬ አልከፋም፥ እንደውም ደስ ይለኛል እንጂ። አንዳንዴ ደግሞ የራሴ ጥፋት እንደሆነ ተቀብያለሁ።
– ምንድነው ያንተ ጥፋት?
* ጥፋቱ አንድ መስመር ከያዝኩ አለቅም ማለቴ ነው። ቢሆንም የሚቆጨኝ አይደለም።
– ምን ያህል አመት በጋዜጠኝነት መያ አገለገልክ?
* ከ1964 አ.ም ጥቅምት ጀምሮ ጡረታ እስከወጣሁበት እስከ 1994 አ.ም የጋዜጠኝነት ስራን ሰርቻለሁ።
– ማስታወቂያ ሚኒስትር በመስራት ጥሩ ስም አግኝተሃል። ነገር ግን በሕይወቴ አሳጣኝ የምትለው ምንድነው?
* በጣም ግሩም ጥያቄ ነው። ተቋሙ ለኔ ብቻ ሳይሆን ለማንኛውም ከላይ እስከታች ላለ ሰራተኛ በሬዲዮም በዜና አገልግሎት ስም አግኝተናል። ያ ስምም ስለሚለጠፍብህ በውጭ ሰዎች እንደ ልዩ ነገር ትታያለህ፡፡ ይሄ ደግሞ አንተ ወደህ ወይም ጠይቀህ የምታመጣው ሳይሆን፥ ከስራው ባህሪ አንጻር ማንኛውም እዚያ ተቋም የሚሰራ ሰው የሚያገኘው ክብር ነው። ግለሰቡ ያን ቦታ ስለሚያውቀው “ለማያውቁሽ ታጠኚ” እንደሚባለው አይነት ነው። የውጪ ሰው ግን አንተ ሁሉ ነገር የተሟላልህና አንዳንዱ ደግሞ እንደመሪ ጓደኛ አድርጎ ይመለከትሃል፡፡ ስም ታገኛለህ ይሄ አይካድም። እርግጥ ጎረምሳ ሳለን ደስ ሊለን ይችል ይሆናል፡፡ እንዲህ ስትሆን ደግሞ ስም ባይኖር ይሻላል ማለት አይቀርም። ቅርብ ጊዜ ከአንድ ግለሰብ ጋር ዘመዴ ቤት ሄጄ፥ “አንተ ብዙ ሰዎች እያወቅህ ለምንድነው ስራ የማታስቀጥረኝ?” ብለውኛል፥ እኔ በውስጤ እንኳን ለሰው ለራሴም አልሆንኩ ብያለሁ።
– ከአንተ በኋላ የመጡ ጋዜጠኞች ሕይወታቸውን በተሻለ ለመምራት በማስታወቂያ ስራ ላይ ተሳትፈዋል። አንተ አሪፍ ድምጽ እያለህ ወደዚህኛው ሰፈር መምጣት ያልፈለከው ለምንድነው?
* በዚህ በኩል ወጣቱን ትውልድ አደንቃለሁ። ሙያውን ይቀስማል፥ ሙያውን ከቀሰመ በኋላ እዚያው ተጋግሮ ተለጥፎ አይቀርም። የራሱን የግል አማራጮች ይፈልጋል፡፡ እኔና የኔ ትውልድ አንድ ተቋም ውስጥ ከገባን በኋላ ወደሌላ መመልከት አይመቸንም ነበር። ማንም ነባር ጋዜጠኛ ብትጠይቅ እንደተጎዳ ፥ እንደተበደለና የሚፈልገውን አላማ ከግብ እንዳላደረሰ ያውቃል። ምክንያቱም የጋዜጠኝነት ስራን መልቀቅ ማለት የህይወት መጨረሻ መስሎ ስለሚታየው ነው፡ ይሄ በነባሩና በአሁን ጋዜጠኞች መካከል ያለው ልዩነት ነው። ማስታወቂያ ያልከኝ እንኳን ያኔ አሁንም መስራት አልፈልግም።
-ለምን?
*እኔ ለረዥም አመታት ዜና ነው ስሰራ የቆየሁት። ዜና ደግሞ በባህሪው ለእውነት የተጠጋ ነው። በዚህ ስራዬ ደግሞ ሶስት መንግስታት ተመልክቻለሁ፡፡ ወደድኩም ጠላሁም በሶስቱም የአገዛዝ ዘመናት የመሪዎቹን ስም የመጥራት እድል ነበረኝ። እንደ መንግስት ቅጥረኛ ጋዜጠኝነቴ ሳገለግል፥ ይሄ ክብርና ጥቅም አለ ተብዬ ሳይሆን ለሚከፈለኝ ደመወዝ፥ ይሄንን አገልግሎት ስጥ ተብዬ የተቀመጥኩ ሰው ነኝ። ስለዚህ እኔ ያንን እንደ ክብር አየዋለሁ። ታዲያ ያንን የሚሰራ ሰው ወርዶ ስለ ክብሪት፥ ስለ ሻማ… ማስታወቂያ መናገር፥ ለእኔ በጣም ስግብግብነትና ራስን ማውረድ ሆኖ ነው የሚሰማኝ።
– ግን እኮ ማስታወቂያ ራሱን የቻለ ሙያ አይደል እንዴ?
* ሙያ መሆኑንማ አልክድም። ጋዜጠኛ ሆኜ እውነቱን ስዘግብ የኖርኩ ሰውዬ የሌለ ነገር መቀባጠር አልፈልግም። በእርግጥ ገንዘብ ሊገኝበት ይችላል፥ ገንዘብ ማግኘት አልጠላም። ግን ገንዘብን በአግባቡና ክብር ባለው መንገድ እንጂ ራሴን አውርጄ አልመኘውም፥ ተመኝቼውም አላውቅም።
– ያንተን መርህ እንደ ሙያ ታማኝነት ማየት ይቻላል?
* ልታየው ትችላለህ።
– ይሄ እኮ የሚያሳየን ለሙያህ ምን ያህል ታማኝ እንደሆንክ ነው?
* በዚህ አልስማማም። ሌላው ደግሞ አጭበርባሪ ነው ሊል ይችላል። አስተያየቱ የአድማጭና የተመልካች ነው እንጂ እኔ ጥሩ ነኝ ብዬ ብናገር ላልሆን እችላለሁ። መጥፎ ነኝ ብል ተቃራኒ ምላሽ ሊገጥመኝ ይችላል።
– መዝናናት ታበዛ ነበር?
* በእርግጥ እስካለሁ በማገኘው ነገር ልደሰት የምል ሰው ነበርኩ። ለምን እከሌ ወደላይ ወጣ ብዬ የምቃጠል ሳልሆን ደስታ የሚሰማኝ ሰው ነኝ። ቅናትንም መንፈሳዊና ተፈጥሯዊ ብላችሁ ለሁለት ከፈላችሁት መሰለኝ!? ለእኔ ግን አንድ ናቸው።
– እንዴት አንድ ናቸው?
* ለእኔ ምንም የሚለያዩበት ነጥብ አላገኘሁባቸውም። ራስን ቆንጆ ለማድረግ ነው መንፈሳዊ ቅናት የሚባለው እንጂ እኔ አንተን ለምን አገኘ? ካልኩ በኋላ ከምቀኛ ውጪ ሌላ ቃል መጠቀም አልፈልግም።
– ጡረታ እስጀወጣህበት ድረስ ደመወዝህ ስንት ነበር? * ደመወዜ 1650 ብር ነበር። ጡረታ ስወጣ 760ብር አገኛለሁ።
– መቼስ በዚህ ገንዘብ የተሟላ ኑሮ እንደማትኖር ይታወቃል፡ ታዲያ ማነው የሚደግፍህ?
* አንዳንድ የሚያውቁኝ ግለሰቦች በሚችሉት መጠን ይረዱኛል። አሁን ለምሳሌ ተክለሃይማኖት አጠቃላይ ሆስፒታል በሰዎች ድጋፍና ጥያቄ ነው የገባሁት።
– በነጻ ሕክምና ማለት ነው?
* እንግዲህ ስፖንሰር እንደሚያደርጉኝ ነው የሰማሁት። ከዚያ ውጪ የማውቀው ነገር የለም።
– በ1978 አ.ም ዜና ስታነብ የፕሬዝዳንት መንግስቱ ሃይለማርያምን ስም በክብር ባለመጥራት የደረሰብህ ችግር እንደነበር ይነገራል እስቲ አጫውተኝ?
* በወቅቱ መንግስቱ ለጉብኝት ውጪ ይሄዳል። ዜና መሰራት ስለነበረበት ሰራነው። መጀመሪያ አርእስተ ዜናውን አነበብኩና ወደ ሃተታው ስገባ እውነቱን ለመናገር ነገሮች ሁሉ ተምታቱብኝ። ድንጋጤና ፍርሃቱ መጣብኝ። መጀመሪያ የፈለገ ነገር ይመጣል እንጄ አነባለሁ ብዬ ወስኜ የነበርኩ ሰው ማንበብ ስጀምር አንዴ ሻለቃ፥ አንዴ ኮሎኔል፥ ሌላ ጊዜ የደርግ ጸሃፊና መንግስቱ እያልኩ ያልቀባጠርኩት ነገር የለም። ይሄ ከሆነ በኋላ ስልክ ተደወለ፡- <<ሰውዬው አብዷል? ምንድነው የምትሰሩት? እንደውም ጥፋተኞች እናንተ ናችሁ፥ ማይክራፎኑን ለምን አትዘጉበትም?>> ብለው ስልኩ ተዘጋ፡፡ ከቢሮ ስወጣ ማስታወቂያ ሚኒስትር በታንክና በመትረየስ ተከቦ ሳይ ደነገጥኩ። ያዙኝና ለሁለት ቀን ያህል አሮጌው አውሮፕላን ማረፊያ የቁም እስረኛ አደረጉኝና ተፈታሁ። ከዚያ ለስድስት ወር ያህል ከስራ ታገድኩ። በኋላ ጠበቃ ይዤ ተከራከርኩና በመጨረሻ ለጊዜው የማላስታውሰው ቅጣት ተጥሎብኝ ወደ ስራ እንድመለስ ተደረኩኝ።
– በጋዜጠኝነት ቆይታህ በሰራኸው ዜና ተቀይሞ ቡጢ የሰነዘረብህ ሰው አላጋጠመህም?
* እንደ ምሳ ባይሆንም የቁርስ ያህል ትንሽ ቀምሻለሁ።
– የአቶ ገዳሙ አብርሃምና የአንተ ጭቅጭቅ ምን ነበር?
* ምንም ነገር የለም። አቶ ገዳሙ በወቅቱ የመምሪይ ሃላፊ ነበር። እኔ ደግሞ ዋና አዘጋጅ ነበርኩ፡፡ ስለዚህ ምንም ቅርበት በሌለበት ደግሞ ጭቅጭቅ አይኖርም።
– ከሌለ ሰራተኛው በሙሉ ለአቶ ገዳሙ የገንዘብ መዋጮ ሲያዋጣ አንተ አይመለከተኝም ለምን አልክ?
* ነገሩ ምን መሰለህ፥ አቶ ገዳሙ ወደ ሌላ መስሪያ ቤት በሹመት ስለሚዘዋወሩ የስንብት ግብዣ በሚል ገንዘብ ይዋጣ ተባለና መሰብሰብ ተጀመረ። አቶ ገዳሙ በጋዜጠኛነት ሙያ በወቅቱ ማንም የሚያህለው አልነበረም፡፡ አስተዳደሩ ላይ ግን በጣም ተንኮለኛ ነበር። የሰው ምንም ጥሩ ነገር አይታየውም። አንዴ ከጠመደ ደግሞ የማይለቅ “አልቅት” አይነት ነገር ነው። የመዋጮ ወረቀት እኔ ጋር ሲመጣ እሺ “0.10 ሳንቲም ጻፊ” አልኳት። ሰብሳቢዋ በድንጋጤ አይን ታየኛለች። ያዋጡትን ሰዎች ዝርዝር ስመለከት ደግሞ አትክልተኛና ዘበኛ ከ20-30 ብር ድረስ መዋጮ ከፍለዋል። ምክንያቱም ገዳሙ የሚፈራ ሰው ነበር። በኋላ ግን ያዋጣነውን መዋጮ ከተመለከቱ በኋላ <<አቅም ስለሌላችሁ መዋጮ አያስፈልግም>> በሚል በደብዳቤ አሳወቁ፡፡ እኔ የተመለከትኩት እንደ ሽሙጥ ነው።
– በአባትህ ኢራናዊ ነህ። አንተ ያለ ስሜት ምንድነው?
* እኔ ተወልጄ ያደኩት አዲስ አበባ ነው። ስለዚህ ስለማላውቀው ሃገር ብትጠይቀኝ ምንም መናገር አልችልም። ኢትዮጲያዊነቴን ከምንም ጋር አላወዳድረውም።
– ግንቦት 13 ቀን 1983 አ.ም፥ ኮ/ል መንግስቱ ሃገር ጥለው ወደ ሐራሬ በሄዱ ጊዜ ማእረጋቸውን ትተህ ማንበብህ ይታወሳል፡፡ ለምን በዚያ መልክ ማንበብ ፈለክ?
* በወቅቱ ለሚኒስትሮች ምክር ቤት የመጣው ዜና፥ ለሕዝብና ለእርሳቸው ደህንነት ሲባል ከአገር እንዲወጡ ተሸኝተዋል የሚል ነበር። ዜናውን ይዞ የመጣውም የወቅቱ ምክትል ሚኒስትር የነበረው መርእድ በቀለ ነበር። በነገራችን ላይ መርእድ በቀለና እኔ አንድ ትምህርት ቤት ነው የተማርነው በጣም ጥሩ ጓደኛዬ ነው፡፡ ጠራኝና “ተሸኝቷል የሚለውን አንብበው ግን ራሱን እንዳታነበው አሻሽለው” ብሎኝ ሊሄድ ሲል፥ “እንግዳው ከሄድክ ሌላውን ዜና እንጂ ይሄንን አላሻሽለውም” አልኩት። “ግዴለህም አንተ የመሰለህን ነገር ስራ” አለኝ። እኔ እንዲያውም እንደ ቀልድ <<ብላቴ የሚገኘው ማሰልጠኛ እሄዳለሁ ብለው አውሮፕላን አስገድደው ወደ ሐራሬ ፈርጥጠው ሄደዋል>> ብዬ ሰርቼ ሰጠሁት። <<በቃ ይሄማ ጥሩ ነው አንብበው>> አለኝ። <<መርዴ ትቀልዳለህ?>> ስለው “አንብበው” የሚል ምላሽ ሰጠኝ፡፡ “ፈርምበት” አለኝ። “እኔ ፈረምኩ አልፈረምኩ ምክትል ሚኒስትር አይደለህ እንዴ?” አልኩት። “አንብበው” አለኝ ገባሁና አነበብኩት።
– ከአነበብከው በኋላ ያገኘኸው ምላሽ ምን ነበር?
* በወቅቱ የተለያየ ስሜት አስተናግጃለሁ፡፡ አንዳንዱ ልክ ነህ ሲለኝ ሌላው ደግሞ ቆይ ጠብቅ ብሎ ይዝትብኝ ነበር።
– አሁን እድሜህ ስንት ደረሰ?
* አሁን 66 አልፌ 67 ልረከብ ነው፡፡
– ስንት ልጆች አሉህ?
* ሰባት ልጆች አሉኝ።
– እንደው ሞት ላንተ ምንድነው? ሞትስ ትፈራለህ?
* ሞት ያለና ሁልጊዜ አብሮ የሚኖር ነው። ስለዚህ ሞት ያሰኘው ጊዜ ይመጣብሃል። በሌላ ጊዜ ደግሞ አስፈራርቶ ይሄዳል። ሞት ከማንኛውም ተፈጥሯዊ ከሆነ ጋር አብሮ ያለ ስለሆነ በበኩሌ ምንም አያስፈራኝም።

የዓመቱ አነጋጋሪና አወዛጋቢ ክስተቶች

$
0
0

በዓመቱ መጀመሪያ በመስከረም ወር 2006 ዓ.ም ለ12 ዓመታት የአገሪቱ ፕሬዚዳንት በመሆን ያገለገሉት ግርማ ወ/ጊዮርጊስ፤ ከስልጣናቸው የወረዱ ሲሆን በቦታቸውም ዶ/ር ሙላቱ ተሾመ ተተክተዋል፡፡ በአምባሳደርነት ዘመናቸው የውጭ አገር ኢንቨስተሮችን ወደ ኢትዮጵያ በማምጣትና አገር ውስጥ መዋዕለ ንዋያቸውን እንዲያፈሱ በማግባባት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ማበርከታቸው የሚነገርላቸው ዶ/ር ሙላቱ፤ የፕሬዚዳንትነት ስልጣናቸውን ከተረከቡ በኋላም ሥራቸው በቤተመንግስት አካባቢ የተገደበ አልሆነም፡፡ በተለያዩ አገራት እየዞሩ የውጭ ኢንቨስተሮችን የማግባባት ሥራቸውን ቀጥለውበታል፡፡
fe32ef4893ac92d41e13984d3a7fb0e2_XL

በዓመቱ ከተከናወኑ አነጋጋሪ ጉዳዮች መካከል አንድነት ፓርቲ ከሰላማዊ ሰልፍ ጋር በተገናኘ የመብት ጥሰትና መጉላላት ተፈጽሞብኛል በማለት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባንና የከተማዋን ፖሊስ ኮሚሽን በፍ/ቤት መክሰሱ ተጠቃሽ ነው፡፡

ፍ/ቤቱም ጉዳዩን ከመረመረ በኋላ “ክሱ ለክስ የሚያበቃ ምክንያት የለውም፣ አስተዳደራዊ ውሣኔ ያገኝ የሚል ውሣኔ የሰጠ ሲሆን ፓርቲውም በጊዜው ይግባኝ እንደሚጠይቅ ገልፆ ይግባኝ ለመጠየቅ በሂደት ላይ ይገኛል፡፡

የቀድሞ የአንድነት ፓርቲ ሊቀመንበር ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ፣ እንዲሁም የኢዴፓ መስራችና ሊ/መንበር የነበሩት አቶ ሙሼ ሰሙ ራሳቸውን ከፖለቲካ ፓርቲ ያገለሉት በዚሁ ባሳለፍነው ዓመት ነው፡፡ ዶ/ር ነጋሶ ከጤና ጋር በተያያዘ፣ አቶ ሙሼ ደግሞ “የጥሞና ጊዜ እፈልጋለሁ” በሚል የፓርቲ ፖለቲካ በቃን ብለዋል፡

ሹመትና ህልፈት
የአማራ ክልልን ለ8 ዓመታት በርዕሰ መስተዳደርነት የመሩት አቶ አያሌው ጎበዜ፣ የደቡብ ክልል ርዕሰ መስተዳደር የነበሩት አቶ ሽፈራው ሽጉጤ በአምባሳደርነትና በትምህርት ሚኒስትርነት የተመደቡት ባሳለፍነው ዓመት ሲሆን የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳደር የነበሩት አቶ አለማየሁ አቶምሳ ባደረባቸው ህመም ህክምና ሲከታተሉ ቆይተው ህይወታቸው ማለፉ ይታወሳል፡፡ በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የህዝብ ተሳትፎና ንቅናቄ ክላስተር አስተባባሪና የሲቪል ሰርቪስ ሚኒስትር የነበሩት አቶ ሙክታር ከድርም የክልሉ ፕሬዚዳንት በመሆን የተሾሙ ሲሆን  በሳቸው ቦታ ወ/ሮ አስቴር ማሞ ተተክተዋል፡፡

የሳኡዲ ስደተኞችን ማባረር
የሳኡዲ አረቢያ መንግስት የመኖሪያ ህጋዊ ፍቃድ የላቸውም በሚል ኢትዮጵያዊያንን ጨምሮ የበርካታ ሃገር ዜጎችን ከሃገሩ በኃይል ማስወጣት የጀመረው ባሳለፍነው ዓመት ጥቅምት ወር  መጨረሻ ገደማ ነበር፡፡ የሳኡዲ አረቢያ መንግስት ህገወጥ ስደተኞች ባላቸው ላይ በወሰደው የማባረር እርምጃ ከ150ሺ በላይ ኢትዮጵያውያን ወደ ሃገር ቤት መመለሳቸው የሚታወስ ሲሆን የዓለም አቀፍ ሚዲያዎችን ትኩረት በሳበው በዚህ ክስተት፣ በተለያዩ የዓለም ክፍሎች የሚገኙ ኢትዮጵያውያን በሳኡዲ ኤምባሲዎች በር ላይ ሰላማዊ ሰልፍ በማድረግ ተቃውሞአቸውን ገልፀዋል፡፡ በአዲስ አበባ ለተመሳሳይ ዓላማ ሰማያዊ ፓርቲ የጠራው ሰላማዊ ሰልፍ ግን በፖሊስ በመበተኑ ሳይደረግ ቀርቷል፡፡

የኢትዮጵያ መንግስት በየአረብ ሃገራቱ ለስራ የሚጓዙ ዜጎች ጉዳይ አሳስቦኛል በማለት ወደ የትኛውም የአረብ ሃገራት ለጉልበት ስራ የሚደረግን ጉዞ ለ6 ወር ያህል ማገዱ የሚታወስ ሲሆን እገዳው 9ኛ ወሩን ቢይዝም እስካሁን አልተነሳም፡፡
“የረዳት አብራሪው የአውሮፕላን ጠለፋ”
በኢትዮጵያ አየር መንገድ ለ5 ዓመታት በረዳት አብራሪነት ያገለገለው ሃይለመድህን አበራ፤ በጥር ወር አጋማሽ ላይ ከአዲስ አበባ ወደ ጣሊያን ሲበር የነበረውን የኢትዮጵያ አየር መንገድ አውሮፕላን  ጠልፎ ስዊዘርላንድ ማሳረፉ ከዓመቱ አነጋጋሪና ትኩረት ሳቢ ጉዳዮች አንዱ ነበር፡፡

ረዳት አብራሪው አውሮፕላኑን ለምን እንደጠለፈ እስካሁንም ይሄ ነው የሚባል አሳማኝ ምክንያት አልተገኘለትም፡፡ የኢትዮጵያ መንግስት ጠላፊው ተላልፎ እንዲሰጠው የጠየቀ ቢሆንም አዎንታዊ ምላሽ አላገኘም፡፡ ጠላፊው የስዊዘርላንድን መንግስት ጥገኝነት ጠይቆ እንደተፈቀደለትና አሁን እዚያው በእስር ላይ እንደሚገኝ ይታወቃል፡፡ ፍትህ ሚኒስቴር በበኩሉ፤ በጠላፊው ላይ  ክስ መስርቶ ፍ/ቤት የአቃቤ ህጎችን ምስክርነት በመስማት  ላይ ይገኛል፡፡

መፍትሔ ያልተበጀለት “የሙስሊሞች ጉዳይ”
“ከሁለት ዓመት በፊት የታሰሩት ሙስሊም መሪዎቻችን ይፈቱ፣ ድምፃችን ይሰማ” የሚሉ ንቅናቄዎች እየተካሄዱ ነው ዓመቱ ያለፈው፡፡ ሐምሌ 11 ቀን 2006 ዓ.ም አርብ በታላቁ አንዋር መስጊድ የተቀሰቀሰውን ተቃውሞ  ተከትሎ ፖሊስ በወሰደው እርምጃ በሰዎች ላይ ድብደባና ጉዳት መድረሱ ይታወሳል፡፡ ቁጥራቸው በውል ያልታወቀ ሰዎች ታስረው የነበረ ሲሆን በነሐሴ ወር መጀመሪያ ላይ በዋስ ተለቀዋል፡፡ ከእነዚህም መካከል የቀድሞው “አዲስ ጉዳይ” መፅሄት የፎቶግራፍ ባለሙያ አዚዛ አህመድ እና የሰማያዊ ፓርቲ አመራር አባል ወይንሸት ሞላ ይገኙበታል፡፡
የታሰሩት ሙስሊሞች ጉዳይ በፍ/ቤት መታየቱን የቀጠለ ሲሆን ተጠርጣሪዎቹ የመከላከያ ምስክሮቻቸውን በማሰማት ሂደት ላይ እንደሆኑ ይታወቃል፡፡

አዲሱ ማስተር ፕላን የቀሰቀሰው ተቃውሞ
ሌላው የዓመቱ አብይ ክስተት የአዲስ አበባና በኦሮሚያ ልዩ ዞን ስር የሚተዳደሩ ከተሞች የጋራ ማስተር ፕላን የተነሳ የተቀሰቀሰው ተቃውሞና ረብሻ ሲሆን የሰው ህይወትን ጨምሮ በርካታ ጉዳትና ውድመት ደርሷል፡፡
በአገሪቱ የተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች የሚማሩ የኦሮሚያ ተወላጅ ተማሪዎች በሚያዚያ ወር አጋማሽ ላይ ባስነሱት ተቃውሞ ሳቢያ ከፖሊስ ጋር ግጭት መፈጠሩ ይታወሳል፡፡
ዓለም አቀፍ ሚዲያዎች በአምቦ ከተማ በተፈጠረው ግጭት 30 የሚደርሱ ሰዎች መሞታቸውን ሲዘግቡ፣ የሃገር ውስጥ መገናኛ ብዙሃን በበኩላቸው፤ በአጠቃላይ የ11 ሰዎች ህይወት ማለፉን ዘግበዋል፡፡
ተቃውሞውን ለማስቆም በፀጥታ ሃይሎች ከተወሰደው እርምጃ ባሻገር ከፍተኛ የመንግስት አመራሮች ውዝግብ ባስነሳው የጋራ ማስተር ፕላን ዙሪያ ከተማሪዎችና ከህብረተሰቡ ጋር ለበርካታ ሳምንታት ውይይት እንዳደረጉም አይዘነጋም፡፡

“አስደንጋጩ” የጋዜጠኞችና ጦማሪያን እስር
መንግስት በሽብርተኝነት ጠርጥሬያቸዋለሁ በማለት  3 ጋዜጠኞችና 6 ጦማሪያን ማሰሩ የዓለም አቀፍ ሚዲያዎችን ትኩረት የሳበ ሌላው የዓመቱ ጉልህ ክስተት ነበር፡፡ አብዛኞቹ ዓለምአቀፍ የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ተቋማትም እስሩን ከመጪው አገራዊ ምርጫ ጋር በማያያዝ የመንግስት ፍርሃት የፈጠረው ጉዳይ እንደሆነ ገልፀዋል፡፡
በሚያዚያ ወር አጋማሽ ላይ ጋዜጠኛ ተስፋለም ወልደየስ፣ ኤዶም ካሳዬ፣ አስማማው ሃይለጊዮርጊስ እንዲሁም “ዞን 9” በተሰኘ ድረገጽ ፀሐፊነታቸው የሚታወቁት አጥናፉ ብርሃኔ፣ ማህሌት ፋንታሁን፣ ዘላለም ክብረት፣ ናትናኤል ፈለቀ፣ በፈቃዱ ሃይሉና አቤል ዋበላ ተይዘው መታሰራቸው የሚታወስ ነው፡
መንግስት በተጠርጣሪዎቹ ላይ በሽብርተኝነት ከተፈረጁ ድርጅቶችና ተቋማት ጋር በመተሳሰር እንደሚሰሩ ደርሼበታለሁ በሚል ክስ የመሰረተባቸው ሲሆን ጉዳያቸው በፍ/ቤት በመታየት ላይ ይገኛል፡፡
የአቶ አንዳርጋቸው መያዝና የተቃዋሚ አመራሮች እስር
በህዝብ ተወካዮች ም/ቤት በአሸባሪነት ከተፈረጁት አምስት የፖለቲካ ድርጅቶች አንዱ የሆነው የ“ግንቦት 7” ዋና ፀሐፊ የነበሩት አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ፣ በሰኔ ወር መጨረሻ ላይ በየመን መያዝና ለኢትዮጵያ መንግስት ተላልፎ መሰጠት የተጠናቀቀው አመት ያልተጠበቀ ክስተት ነበር፡፡ የእንግሊዝ ዜግነት ያላቸው አቶ አንዳርጋቸው፤ ቀደም ሲል በሌሉበት በተመሰረተባቸው የአሸባሪነት ክስ የሞት ፍርድ እንደተወሰነባቸው ይታወሳል፡፡

እኚህ የግንቦት 7 ከፍተኛ አመራር በኢትዮጵያ መታሰራቸውን ተከትሎ በተለያዩ የአሜሪካና አውሮፓ አገራት የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን በእንግሊዝ ኢምባሲዎች ደጃፍ ላይ በመሰባሰብ ተቃውሞ ማሰማታቸውን ቀጥለዋል – እንግሊዝ ዜግነት ለሰጠችው ሰው ተገቢውን ጥበቃና ከለላ አልሰጠችም በሚል፡፡
አንዳንዶች እንደሚሉት፤ የአቶ አንዳርጋቸው ጦስ ለአገር ውስጥ የተቃዋሚ ፓርቲ አመራሮችም ተርፏቸዋል፡፡ እሳቸው በታሰሩ ማግስት በሐምሌ ወር መጀመሪያ ላይ የአንድነት ፓርቲ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ሃብታሙ አያሌውና የፓርቲው የድርጅት ጉዳይ ም/ኃላፊ አቶ ዳንኤል ሺበሺ፣ የሰማያዊ ፓርቲ ብሄራዊ ም/ቤት ም/ሰብሳቢ አቶ የሽዋስ አሰፋ እንዲሁም የአረና ፓርቲ አመራር አባል አቶ አብርሃ ደስታ በሽብር ተጠርጥረው የታሰሩ ሲሆን ጉዳያቸውም በፍ/ቤት እየታየ ነው፡፡
የግል የሚዲያ ተቋማት ክስ፤ የአሳታሚዎችና ጋዜጠኞች ስደት
መንግስት በ“ፋክት” ፣ “ሎሚ” ፣ “አዲስ ጉዳይ”፣ “እንቁ”፣ “ጃኖ” መፅሄት እና “አፍሮ ታይምስ” ጋዜጣ አሳታሚዎችና ባለቤቶች ላይ የወንጀል ክስ መመስረቱን በቴሌቪዥን የገለፀው  በሐምሌ ወር መጨረሻ ነበር፡፡ ከመግለጫው ጥቂት ሳምንት በኋላ ለፍ/ቤት የቀረበው የአሳታሚዎችና የስራ አስኪያጆቹ ክስ ጠቅለል ብሎ ሲታይ በተለያዩ የህትመት ውጤቶቻቸው በፃፏቸው ፅሁፎች በህገ-መንግስታዊ ስርአቱ ላይ አመፅ ቀስቅሰዋል፣ በሃሰት ወሬ ህዝብን በመንግስት ላይ የሚያነሳሱ ፅሁፎችን አትመዋል የሚል ሲሆን የፍ/ቤት ሂደቱም ቀጥሏል፡፡
የመንግስትን ክስ ተከትሎ ከ “ፋክት” መፅሄት አሳታሚ በስተቀር የሁሉም ተከሳሽ የሚዲያ ተቋማት ባለቤቶች ሃገር ለቀው የወጡ ሲሆን በአጠቃላይ 16 ያህል የግል ፕሬሱ አባላት አገር ለቀው ተሰደዋል፡፡ መንግስት በበኩሉ፤ በጋዜጠኞች ላይ የተመሰረተ ክስ ስለሌለ የተሰደደ አንድም ጋዜጠኛ የለም ብሏል፤ ጋዜጠኞቹ ለተሻለ ኢኮኖሚያዊ ጥቅም ከአገር መውጣታቸውን በመጠቆም፡፡
“ብዙ የተባለለት የደሞዝ ጭማሪ”
ብዙ የተነገረለትና በጉጉት የተጠበቀው የመንግስት ሰራተኞች የደሞዝ ጭማሪም የተደረገው በዚህ ዓመት ሐምሌ ወር ጀምሮ ነው፡፡ ጭማሪው ከፍተኛ ይሆናል በሚል ግምት ከፍተኛ የመነጋገሪ አጀንዳ ሆኖ የቆየው የደሞዝ ጭማሪው ብዙዎች እንደጠበቁት ግን አልሆነም፡፡ ጭማሪው ከ33 እስከ 46 በመቶ ብቻ ነበር፡፡ ጭማሪውን ተከትሎም ነጋዴው በመሰረታዊ ሸቀጦች ዋጋ ላይ ጭማሪ እንዳያደርግ መንግስት ተደጋጋሚ ማስጠንቀቂያ ሲሰጥ ቆይቷል፤ ማስጠንቀቂያውን የጣሱ “ህገወጥ” ነጋዴዎች ላይም እርምጃ መወሰዱን መንግስት አስታውቋል፡፡
“ዓለምን ያስደነገጠው ኢቦላ”
በምዕራብ አፍሪካ አገራት ተከስቶ ወደሌሎች የአፍሪካ አገራት የተስፋፋው ኢቦላ፤ መላውን ዓለም ድንጋጤ ውስጥ የከተተው በዚሁ ዓመት ላይ መገባደጃ ላይ ሲሆን አሁንም ስጋት እንደሆነ ቀጥሏል፡፡
ዓለም አቀፉ የጤና ድርጅት (WHO) ከትላንት በስቲያ ይፋ ባደረገው መረጃ፤ ቫይረሱ በተከሰተባቸው የአፍሪካ አገራት 2ሺ ገደማ ሰዎች ለህልፈት መዳረጋቸውን አስታውቋል፡፡
ኢትዮጵያም የዚህ ቫይረስ ተጠቂ እንዳትሆን ከወዲሁ ለመከላከል የተለያዩ የቅድመ ጥንቃቄ እርምጃዎች እየተወሰዱ መሆኑን መንግስት አስታውቋል፡፡ ቦሌ አየር መንገድን ጨምሮ በተለያዩ የድንበር አካባቢዎች ጊዜያዊ የምርመራ ጣቢያዎች የተቋቋሙ ሲሆን በአዲስ አበባም 50 አልጋዎች ያሉት ልዩ ሆስፒታል መዘጋጀቱን የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡

ምንጭ፡ አዲስ አድማስ


የድንበር ተሻጋሪ ጉዲፈቻ ታሪካዊ አጀማመር

$
0
0

*ጦርነት፣በሽታ፣ድህነት– ለድንበር ተሻጋሪ ጉዲፈቻ መስፋፋት አስተዋጽኦ አበርክተዋል

“ድንበር ተሻጋሪ ጉዲፈቻ”የሚለውን አጠራር የተባበሩት መንግስታት ዓለምአቀፍ የህፃናት ፈንድ(ዩኒሴፍ)፤ ልጆች ከትውልድ አገራቸው ድንበር ተሻግረው ወደ ሌላ አገር በመግባትበጉዲፈቻ የሌላ ቤተሰብ አባል የሚሆኑበት ሁኔታ ነው ሲል ይተረጉመዋል

BAD392AE-8998-410B-986B-F186C0C498E5_w640_r1_sበተለያዩ አገራት ዜጐች መካከል የሚፈፀም ጉዲፈቻ እየጨመረ የመጣው ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት ማብቂያ በኋላ ነው፡፡ በዚህ ጦርነት የተነሳ አያሌ ህፃናት ወላጆቻቸውን በማጣታቸው፤በማሳደጊያዎች ውስጥበአሰቃቂ ሁኔታ ተይዘው ለማደግ ይገደዱ ነበር፡፡ከዚያ የተሻለ ሌላ አማራጭም አልነበራቸውም፡፡

ድንበር ተሻጋሪ ጉዲፈቻ የተጀመረው የተለያዩ አገራት ወታደሮች የጦርነት ቀጠና በሆኑ የዓለም አገራት መስፈራቸውን ተከትሎ እንደሆነ መረጃዎች ይጠቁማሉ፡፡ ሁለተኛው የዓለም ጦርነት ካበቃ በኋላ በበርካታ የአለም ክፍሎች የተነሱ ግጭቶች ለወታደሮች በየአገሩ መስፈር ምክንያት ሆኗል፡፡ በተለይ የተባበሩት መንግስታት ወታደሮች በኮሪያ ጦርነት እንዲሁም የአሜሪካ ወታደሮች በቬትናም ውጊያ ወቅት በርካታ ልጆችን እንደወለዱ መረጃዎች ያመለክታሉ፡፡

በአብዛኛው ጉዲፈቻ የተደረገው ወደ አሜሪካ እና አውሮፓ አገራት ሲሆን የጉዲፈቻ ልጆች ምንጭ አገሮችም ደቡብ ኮሪያ፣ ቬትናም እና የመሳሰሉት ነበሩ፡፡ ከጦርነትና ግጭቶች በተጨማሪም ድርቅ፣ በሽታና ድህነትም ለድንበር ተሻጋሪ ጉዲፈቻ መስፋፋት ምክንያት ሆነዋል፡፡

ለዚህም ሩሲያ፣ ጉዋቲማላ፣ ቻይና እና የአፍሪካ አገራት ይጠቀሳሉ፡፡
በተለይ ከደቡብ ኮሪያ በርካታ ቁጥር ያላቸው ህፃናት በጉዲፈቻ የተወሰዱ ሲሆን ለዚህም ምክንያቱ በሰሜኑና ደቡብ መካከል በተደረገው በርካታ አገሮች የተሳተፉበት ጦርነት፣ ልጆች ቤተሰባቸውን በማጣታቸው ነው፡፡ ከዚህም ሌላ በወቅቱ በደቡብ ኮሪያ ሰፍረው ከነበሩ የአሜሪካ ወታደሮች የተወለዱ ህጻናት በመልክ ከአካባቢው ማህበረተሰብ የተለዩ ስለነበሩ፣ለማህበራዊና ስነልቦናዊ ችግሮች ተጋልጠዋል፡፡እነሱ ብቻ ሳይሆኑ እናቶቻቸውም በሕብረተሰቡ ዘንድ መገለል ይፈጸምባቸው ነበር፡፡በጦርነት ሰበብ የተወለዱ ህፃናት በአብዛኛው በጉዲፈቻ የሚወሰዱት ወደ አባቶቻቸው አገር ሲሆን ለዚህም ምክንያቱ በአባታቸው የዜግነት መብት ስላላቸው ነው፡፡ ይሔም ለድንበር ተሻጋሪ ጉዲፈቻ መጨመር አስተዋጽኦ አድርጓል፡፡ ከዚህም ባሻገር“በጦርነት ምክንያት የተወለዱ ልጆች በመሆናቸው ልንታደጋቸው ይገባል”የሚለው አስተሳሰብ ድንበር ተሻጋሪ ጉዲፈቻን ያስፋፋ ሲሆን “ጉዲፈቻ በአገሮች መካከል መልካም ግንኙነት ለመፍጠርም ይረዳል”የሚለው አመለካከት ስር መስደዱ ሌላው ምክንያት ነው ሊባል ይችላል፡፡

በአሜሪካ ድንበር ተሻጋሪ ጉዲፈቻ ተቋማዊ በሆነ መልኩ የተጀመረው እ.ኤ.አ. በ1956 ዓ.ም ሆልት በሚባል በጎ አድራጊ ግለሰብ ሲሆን በአሁኑ ወቅት “ሆልት ችልድረንስ ሰርቪስ” በበርካታ አገራትየሚንቀሳቀስና ብዙ ቅርንጫፎች ያሉት የጉዲፈቻ አገልግሎት ኤጀንሲ ለመሆን በቅቷል፡፡ ኤጀንሲው ኢትዮጵያ ውስጥ መስራት ከጀመረም ከሰባት ዓመት በላይ አስቆጥሯል፡፡
በተለያዩ አገራት የተከሰቱ ማሕበራዊ፣ ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ቀውሶችምለድንበር ተሻጋሪ ጉዲፈቻ መስፋፋት አስተዋጽኦ አድርገዋል፡፡

በሮማኒያ የቻችስኩ መንግስት ፖሊሲ /Ceausescu’s Policy/ እያንዳንዷ ሩማንያዊት ሴት፣ቢያንስ አምስት ልጅ የመውለድ ግዴታ ተጥሎባት ነበር፡፡ አንዳንድ ቤተሰቦች ታዲያበድህነት የተነሳ የወለዷቸውን ልጆች ማሳደግ ስለማይችሉ ህጻናት ማሳደጊያ ውስጥ ለማስገባት ይገደዱ ነበር፡፡ የቻችስኩ መንግስት እ.ኤ.አ. በ1989 ዓ.ም በወደቀ ማግስት፣በአገሪቷ ውስጥ ከስድስት እስከ ስምንት መቶ የሚደርሱ የህፃናት ማሳደጊያዎች ነበሩ፡፡በእያንዳንዱ ማሳደጊያም ከ100ሺ እስከ 300ሺ የሚገመቱ ህፃናትእንደነበሩ መረጃዎች ይጠቁማሉ፡፡ በማሳደጊያዎች ውስጥ ያሉ ህፃናት ሁኔታበመገናኛ ብዙሃንበሰፊውይነገር ስለነበር፣ አሁንም “ልጆችን ልንታደጋቸው ይገባል” በሚል ዓላማ፣የምእራቡ አለም ድንበር ተሻጋሪ ጉዲፈቻን ማድረጉን ቀጠለበት። በተመሳሳይ ሁኔታ በሩሲያ በነበረው ከፍተኛ የሆነ ድህነት የተነሳም ከ300ሺ በላይ ህፃናት ማሳደጊያ ውስጥ እንዲገቡ ምክንያት ሆኖ ነበር፡፡ ይሄን ተከትሎም የድንበር ተሻጋሪ ጉዲፈቻ ሊጨምር ችሏል፡፡

በቻይና አሁንም ድረስ የሚተገበረውና የህዝብ ብዛትን ለመቀነስ በመንግስት የወጣው አንድ ልጅ ብቻ የመውለድ ፖሊሲ፣ ዜጎች ጉዲፈቻ እንዳያደርጉ ከተቀመጠው ክልከላ እንዲሁም ህብረተሰቡ “ወንድ ልጅ ቤተሰቡን ይጦራል” በሚል ለሴት ህፃናት ባለው አሉታዊ አመለካከት የተነሳ፣ ብዙ ልጆች በተለይም ሴት ልጆች ማሳደጊያ ውስጥ እንዲገቡ ተገደዋል፡፡

የኤችአይቪ/ ኤድስ መስፋፋትምለድንበር ተሻጋሪ ጉዲፈቻ መጨመር ትልቅ አስተዋፅኦ እያደረገ ይገኛል፡፡ ከሰሃራ በታች ባሉ የምስራቅ አፍሪካ አገራት 12.3 ሚሊዮን ህፃናት በኤድስ ምክንያት ወላጆቻቸውን እንዳጡ ይገመታል፡፡ ሆኖም በአፍሪካ ድንበር ተሻጋሪ ጉዲፈቻ እንደሌሎች የዓለም አገራት በብዛት አልተለመደም፡፡ ለዚህ ምክንያቱ ደግሞ በአህጉሪቱ ልጆችን በቤተዘመድ የማሳደግባህል መኖሩ ሳይሆን እንደማይቀር ይገመታል፡፡ አሁን ባለው ተጨባጭ የአህጉሪቱ የኢኮኖሚ ሁኔታ ግንወላጆቻቸውን ያጡ ህፃናት በቤተዘመድ የማሳደግ ሁኔታ መቀጠሉ በእጅጉ የሚያጠራጥር ነው፡፡ እናም በአፍሪካ ድንበር ተሻጋሪ ጉዲፈቻ እየተስፋፋ እንደሚመጣ ጥናቶች ይጠቁማሉ፡፡

ድንበር ተሻጋሪ ጉዲፈቻ፤ ዝምድና በሌላቸው ሰዎች መካከል የሚደረግ የጉዲፈቻ ዓይነት በሚለው ዘርፍ የሚመደብ ነው፡፡ የዚህ ዓይነት ጉዲፈቻ ልጁ የተፈጥሮ ልጅ አለመሆኑ ብቻ ሳይሆን በጉዲፈቻ አድራጊዎችናበጉዲፈቻ ተደራጊ መካከል የድንበር፤ የቀለም፣ የባህል፣ የዘር፣የማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ልዩነትምየሚስተዋልበት መሆኑ ነው፡፡

የድንበር ተሻጋሪ ጉዲፈቻ፤ መንግስት ወላጅ ለሌላቸው ህጻናት ከሚያቀርበው አማራጭ የእንክብካቤ መንገዶችአንዱ ሲሆን ጉዲፈቻው ፐብሊክ /public adoption/ በሚለው ዘርፍ ይመደባል፡፡ ይህም ለጉዲፈቻ የሚቀርቡት ልጆች ዕጣ ፈንታየሚወሰነው በሚመለከተው የመንግስት አካል መሆኑንያመላክታል።

ምንጭ፡ አዲስ አድማስ

ከንግድ ባንክ ከሰባት ሚሊዮን ብር ላይ በመመዝበር የተጠረጠሩ ኃላፊዎች ተከሰሱ

$
0
0

- ተጠርጣሪዎቹ በጋብቻና በሥጋ ዝምድና የተሳሰሩ ናቸው ተብሏል

CBE_SAበኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ዋናው መሥሪያ ቤት በሒሳብ ማስታረቅ ሥራ ክፍል የደንበኞች አገልግሎት ሥራ አስኪያጅና የሒሳብ አስታራቂ ሲኒየር ኦፊሰርን ጨምሮ 13 ተጠርጣሪዎች፣ ከሰባት ሚሊዮን ብር በላይ ከባንኩ የውስጥ ሒሳብ በመመዝበር ወንጀል ተጠርጥረው ክስ ተመሠረተባቸው፡፡

የፌዴራል የሥነ ምግባርና የፀረ ሙስና ኮሚሽን ዓቃቤ ሕግ ነሐሴ 28 ቀን 2006 ዓ.ም. በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ተረኛ ችሎት ክስ ያቀረበባቸው፣ የንግድ ባንክ ዋና መሥሪያ ቤት የሒሳብ ማስታረቅ የደንበኞች አገልግሎት ሥራ አስኪያጅ አቶ ታምርአየሁ ተክሌና የሒሳብ አስታራቂ ከፍተኛ ኦፊሰር አቶ ኤፍሬም ወልደተንሳይ ናቸው፡፡

የአቶ ታምራየሁ አማች ናቸው የተባሉት አቶ ንብረት ማሞና እህቶቻቸው ወ/ሮ ትንሳኤ ማሞ (የአቶ ታምራየሁ ሚስት)፣ ወ/ሮ ውዳሴ ማሞ፣ የአቶ ኤፍሬም ወንድም አቶ ሔኖክ ወልደተንሳይና የአቶ ታምራየሁ አክስት ልጅ ናቸው የተባሉት ተጠርጣሪ አቶ ዓለሙ አብርሃም (ያልተያዙ) በዋና ወንጀል አድራጊነት የተጠረጠሩ ናቸው፡፡ በአቶ ንብረት ማሞ ሥራ አስኪያጅነት የሚመሩና አድራሻቸው በሐዋሳ የሆነ ጂቢሲ ጠቅላላ ኮንስትራክሽን ማኅበር፣ ንብረት ማሞ ጠቅላላ ኮንስትራክሽን ድርጅት፣ በአቶ ታምራየሁ ሥራ አስኪያጅነት የሚመራው አዳነና ቤተሰቦቹ የኮንስትራክሽን ማሽነሪ አከራይ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማኅበር፣ በአቶ ሔኖክ ሥራ አስኪያጅነት የሚመራው ሔኖክ ወልደተንሳይ ኮንስትራክሽን ማሽነሪ አከራይ ድርጅትና በአቶ ዓለሙ ሥራ አስኪያጅነት የሚመራ ወንድገማኝ ዴዛ ሕንፃ ሥራ ኮንስትራክሽን ድርጅትም በክሱ ተካተዋል፡፡

በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ዋናው መሥሪያ ቤት፣ በሒሳብ ማስታረቅ ሥራ ላይ የነበሩት ኃላፊዎች አቶ ታምራየሁና አቶ ኤፍሬም፣ ከሌሎቹ ተጠርጣሪዎች ጋር በሥጋና በጋብቻ ዘመዳሞች መሆናቸውን የሚጠቁመው የዓቃቤ ሕግ ክስ፣ ይኼም ግንኙነታቸው ወንጀሉን ለመፈጸምና ሚስጥሩን ለመጠበቅ መልካም አጋጣሚ ስለፈጠረላቸው፣ የማይገባ ጥቅም ለማግኘትና ለሌሎች ለማስገኘት በማሰብ፣ ከባንኩ የውስጥ ሒሳብ ላይ 7,064,857 ብር መመዝበር በመንግሥት ላይ ጉዳት ማድረሳቸውን ክሱ ያብራራል፡፡

ገንዘቡ ሊመዛበር የቻለው ሁለቱ የባንኩ ኃላፊዎች የተሰጣቸውን ኃላፊነት በመጠቀም ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ዋናው መሥሪያ ቤት የውስጥ ሒሳብ ላይ በመቀነስ፣ በተለያዩ የባንኩ ቅርንጫፎች መተላለፍ የሚገባቸውን የሒሳብ ማስታረቅ ሥራዎች፣ የሥራ ኃላፊነትን ወደ ጎን በመተው ለጥቅም ሲሉ መመሳጠራቸውን ክሱ ያስረዳል፡፡

በመሆኑም ገንዘቡን በስውር ለመመዝበር እንዲያስችላቸው ከአቶ ንብረት ማሞና ከአቶ ዓለሙ አብርሃም ጋር በጥቅም በመመሳጠር የአቶ ኤፍሬምን የግል መግቢያ ቃል (User Name) እና የሚስጥር ቃል (Password) በሕገወጥ መንገድ በመጠቀም ወጪ ማድረጋቸውን ክሱ ይዘረዝራል፡፡

ሁለቱ የባንኩ ኃላፊዎች የክሬዲት ሒሳብ ትኬት አዘጋጅተው በመፈረምና የባንኩን ሠራተኞች የባንክ ሲስተም የግል መግቢያ ቃልና የሚስጥር ቃል በመጠቀም፣ ገንዘቡን በተለያየ መጠን ወጪ ማድረጋቸውን ክሱ ያስረዳል፡፡

ከባንኩ የውስጥ ሒሳብ ላይ ያላግባብ ወጪ በማድረግ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሐዋሳ ዲስትሪክት ታቦር ቅርንጫፍ፣ አቶ ንብረትና ወ/ሮ ውዳሴ መሥራች በመሆን ባቋቋሙት ጂቢሲ ጠቅላላ ኮንስትራክሽን ስም በተከፈተ አካውንትና በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጠመንጃ ያዥ ቅርንጫፍ በሚገኘው ወንድማገኝ ዴዛ ሕንፃ ኮንስትራክሽን ስም በተከፈተ አካውንት፣ በድምሩ 7,064,857 ብር በሕገወጥ መንገድ እንዲዛወር ማድረጋቸውን ክሱ ያብራራል፡፡

አቶ ንብረት የተባሉት ተጠርጣሪ ከወ/ሮ ውዳሴ ጋር በጋራ ባቋቋሙት ድርጅት ስም፣ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ዋናው መሥሪያ ቤት ሒሳብ ላይ እየተቀነሰ ሐዋሳ በሚገኘው የባንኩ ታቦር ቅርንጫፍ በሁለቱ የባንኩ ኃላፊዎች አማካይነት ሲተላለፍላቸው እንደነበር፣ በአቶ ኤፍሬም ስም በኅብረት ባንክ መስቀል ፍላወር ቅርንጫፍ በከፈቱት ሒሳብ ሲያስተላልፉ እንደነበር፣ በአቶ ሔኖክ ስም በዳሸን ባንክ መስቀል ፍላወር ቅርንጫፍ ሲተላለፍ እንደነበር፣ በወ/ሮ ትንሳኤ ስም በዳሸን ባንክ ዓቢይ ቅርንጫፍ በተከፈተ ሒሳብ ሲተላለፍ እንደነበርና በሌሎቹም ግለሰቦችና ድርጅቶች ስም በተለያዩ ባንኮች በተከፈቱ አካውንቶች ገንዘቡን ሲያስተላልፉ እንደነበር ክሱ ይገልጻል፡፡

ተጠርጣሪዎቹ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በተለያዩ አካውንቶች ወጥቷል የተባለውን ከሰባት ሚሊዮን ብር በላይ ገንዘብ የተለያዩ የኮንስትራክሽን ማሽነሪዎች፣ ደረቅ የጭነት ማመላለሻ ገልባጭ መኪና፣ ጅምር ቤት፣ የቤት አውቶሞቢሎችና ሌሎች ንብረቶችን መግዛታቸውንና በሕገወጥ መንገድ የተገኘን ገንዘብ ሕጋዊ አስመስለው በማቅረብ ሲገለገሉበት እንደነበር ክሱ ያስረዳል፡፡

በአጠቃላይ ተጠርጣሪዎቹ ሁለት ክስ የቀረበባቸው ሲሆን አቶ ታምራየሁ፣ አቶ ኤፍሬም (ያልተያዙ)፣ አቶ ንብረት፣ አቶ ሔኖክ፣ ወ/ሮ ትንሳኤ፣ ወ/ሮ ውዳሴ (ያልተያዙ)፣ አቶ ዓለሙ (ያልተያዙ) በመንግሥት ላይ ጉዳት በማድረሳቸውና ያላግባብ ተጠቃሚ በመሆናቸው በዋና ወንጀል አድራጊነትና በልዩ ወንጀል ተካፋይነት በፈጸሙት በሥልጣን ያላግባብ መገልገል ወንጀል መከሰሳቸውን ክሱ ያብራራል፡፡

በሌላ በኩል ሁሉም ተጠርጣሪዎች ያገኙትን ገንዘብ ሕገወጥ አመጣጡና ምንጩን በመደበቅና በመሸፈን፣ ሕጋዊ አስመስሎ ለማቅረብና ከወንጀል ተጠያቂነት ለማምለጥ፣ የገንዘቡን እንቅስቃሴ ሰውረው በማዘዋወር በፈጸሙት፣ በወንጀል የተገኘን ገንዘብ ሕጋዊ አስመስሎ ማቅረብ የሙስና ወንጀልም መከሰሳቸውን ክሱ በዝርዝር ያስረዳል፡፡

Source:: Ethiopian Reporter

የአፋርን ሕዝብ ወኃ ጠማው

$
0
0

አኩ አብን አፋር ለዘ-ሐበሽ አንደዘገበው፦

በአፋር ክልል በ32 ወረዳዎች ህዝብ በውኃ ጥም በከፈተኛ ችግር ውስጥ ይገኛል። ባለፉት 5 አመታት ለኢህአዴግ ባለስልጣናት ኢንቨስትመንት ተብሎ ከህዝቡ የተቀማው የአፋር ህዝብ መሬት ለህዝብ በከፍተኛ ደረጃ የውኃ እጥረት አስከተሏል!! በአዋሽ ወንዝ ዳር ሲኖሩ የነበሩ አርብቶ አደሮች በግዴታ በመንደር በማሰባሰብ ከፍተኛ ኪሳራ በህዝቡ ላይ አድርሷል።

(ፎቶ ፋይል)

(ፎቶ ፋይል)


ለምሳሌ ፦ በግብርና አስተዳደር የነበረው ህዝብን በግዴታ በመንደር በመሰብሰብ ለከፍተኛ አደጋ እያጋለጡ ነው። ትምህርት ፣ ህክምና፣ ኤሌክትሪክ፣ ውኃ እና የመሳሰሉትን ነገሮች ሳይዘጋጀላቸው ህዝብን እያፈናቀሉ ነው። በአሁኑ ወቅት በጭፍራ ወረዳ «በወአማ» ቀበሌ የሚገኙ ህዝቦች በመጀመሪያ በመንግስት የተሰበሰቡ ሲሆኑ በአሁኑ ወቅት ግን ከመንግስት ልያገኙ የሚገባቸውን ነገሮች እንደማያገኙ ይናገራሉ። ከጭፍራ ፣ከሚሌ፣ ከገዋኔና አካባቢው ወጣቶች ለስደት ወደ ጅቡቲ እንዲሁም ወደ አረብ ሃገራት እየተሰደዱ መሆናቸው ይደመጣል።

በጣም ነው የሚያሳዝነው በሎግያ አካባቢ አንድ ጄርካን ውኃ በ17 ብር እየገዙ የሚጠጡ አሉ! «የክልሉ መንግስት ምን እየሰራ ነው? እኛ መንግስት የለንም! መንግስት የራሱን የስልጣን እድሜ ለማራዘምና ለቤተሰቦቻቸውን ብቻ ለመርዳት የሚሰራ የሙስና ቡድን እንጂ መንግስት የለንም» ሲሉ ብዙዎች ይናገራሉ!! ህክምና ለማግኘት ወደ ደሴ መሄድ አለባቸው ወደ ደሴ በመሄድ መንገድ ላይ የሚሞቱም አሉ! ከ4 ወር በፊት አንዲት አዛውንት በእባብ ተነድፈው ወደ ደሴ ሆስፒታል እየወሰዷቸው መንገድ ላይ ህይወታቸው አልፏል! «እውነት ለመናገር የአፋር ክልል ችግር ከሌሎች የኢትዮጵያ ክልሎች የተለየ ነው» ሲሉ ነዋሪዎች ብሶታቸው ይናገራሉ። «ክልሉ እየተመራ ያለው ኃላፊነት በማይሰማቸው መሀይሞች በመሆኑ ነው ከአሁን በኋላ የምንጠበቀው እድገት የለም» ይላሉ ነዋሪዎቹ።

በአፋር ክልል 32 ትላልቅ ወረዳዎች ይገኛሉ፣ በመላው የአፋር ክልል ብቸኛው እና እድሜ ጠገብ የሆነው አንድ ሆስፒታል አለ፤ እሱም የተገነባው በደርግ ጊዜ ነው። በዱብቲ የሚገኘው ይህ ሆስፒታል ለህዝብ የሚሰጠው አገልግሎት በጣም አነስተኛ ነው! የወባ መድኃኒት እንኳን አይገኝበትም የዱብቲ ወረዳ ነዋሪዎች እንደሚሉት ከሆነ ለሆስፒታሉ የሚሰጠው ማቴሪያልና መድኃኒቶች ለግል ፋርማሲዎች ይሸጣሉ።

በኢትዮጵያውያን ተቃውሞ የተነሳ የሥርዓቱ አሽከር የሆነው የሸዋፈራው የኮሜዲ ሾው ተሰረዘ

$
0
0

(ዘ-ሐበሻ) የሕወሓት ኢሕአዴግን አስተዳደር ደግፎ በስደት የሚገኘውን ኢትዮጵያዊ በሕዝብ ፊት ተሳድቦ ከመንግስት ባለስልጣናት ፍርፋሪ ለማግኘት ሲሰራ የቆየው ሸዋፈራው ደሳለኝ በዋሽንግተን ዲሲ ሰድቦ ለሰዳቢ ለሰጠው ሕዝብ ትያትር ለማሳየት የመጣ ቢሆንም ዝግጅቱ ሳይደረግ መሰረዙ ተሰማ።
shewaferaw
ከዋሽንግተን ዲሲ የዘ-ሐበሻ ዘጋቢዎች እንዳስታወቁት የወያኔ/ኢሕአዴግ አሽከር የሆነው አርቲስት ሸዋፈራው ደሳለኝ በአሁኑ ወቅት የኢትዮጵያውያኑን አይን ፈርቶ ተደብቆ የሚገኝ ሲሆን በየሄደበት ቦታ ሁሉ በሚደርስበት ተቃውሞ በከፍተኛ የስነልቦና ቀውስ ውስጥ መውደቁ ተሰምቷል።

መንግስትን ለማገልገል ሲል በስደት የሚገኘውን ሕዝብ ተሳድቦ፤ በዚሁ ሕዝብ ላይ ገንዘብ ለመሥራት የመጣው ሸዋፈራው ወደ አሜሪካ ከመምጣቱ በፊት በሃገር ቤት የሚገኙ የተለያዩ ሴት አርቲስቶችን “አሜሪካ እወስዳችኋለሁ፤ እዛ ሄደን በየ ስቴቱ ትያትር እናሳያለን” በሚል ቃል በመግባት ሴትነታቸውን ለመጠቀም ባደረገው ግፍ አርቲስቶቹ ከፍተኛ ሃዘን ውስጥ መውደቃቸው የተሰማ ሲሆን እዚህ ከመጣ በኋላ ትያትሩን ሊያቀርብ ሲል በተቃውሞ መመታቱ በሃገር ቤት የተበደሉትን ሁሉ እንዳስደሰተ ምንጮች ጠቁመዋል።

ዛሬ እሁድ በዋሽንግተን ዲሲ ይደረጋል በተባለው የሸዋፈራው ኮሜዲ ሾው ላይ በዲሲ የሚገኙ ታዋቂ አክቲቪስቶች “ካሁን በኋላ ትዕግስታችን ተሟጧል፤ የወያኔ ተላላኪዎች እንደፈለጉት አይጨፍሩብንም” በሚል በጠሩት ቦይኮት የተነሳ ዝግጅቱ ተሰርዟል። ለዚህ ዝግጅት ከቪዛና ከትራንስፖርት ጀምሮ በብዙ ሺህ የሚቆጠሮ ዶላሮች የፈሰሱ ሲሆን በኪሳራ ሊሰረዝ በቅቷል።

ከወያኔ ጋር በመተባበር ለሆዳቸው ያደሩ አርቲስቶች በዲያስፖራው ከፍተኛ ኪሳራ እየደረሰባቸው ሲሆን ሃመልማል አባተ ለሲዲ ምርቃት በጠራችው ኮንሰርት በደረሰባት ቦይኮት 55 ሰው ብቻ ተገኝቶ አፍራ ወደ ሃገር ቤት መመለሷ መዘገቡ አይዘነጋም።

ሸዋፈራው ከዲያስፖራው አፍሰዋለው ያለው $$$ በዲሲ እንዲህ ያለው እክል ያጋጠመው ሲሆን በሌሎች ስቴቶች እንኳን የኮሜዲ ሾው አደርጋለሁ ቢል በየቦታው ባሉ የድጋፍ ሰጪዎች ከፍተኛ የሆነ ችግር እንደሚገጥመው ከወዲሁ እየተነገረ ነው።

ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ዲያፖራው ሕዝብን እየጨፈጨፈ ከሚገኘው መንግስት ጎን ለቆሙ ሆዳም አርቲስቶች ያለው ትዕግስት ተሟጦ ማለቁ ከሚደረጉት እንስቃሴዎች እየታየ ነው።

ሶስት ጋዜጠኞች አገር ለቀው ወጡ

$
0
0

የወያኔው መንግስት አላሰራ ያላቸው እና ጫናውን ያሳረፈባቸው ሶስት ጋዜጠኞች አገር ለቀው መውጣታቸው ታውቋል።
በዚህም መሰረት

1ኛ/ ሚሊዮን ሹሩቤ – የማራኪ መጽሄት ባለቤት እና አዘጋጅ
2ኛ/ ኤሊያስ ጉዲሳ – የቃልኪዳን መጽሄት ባለቤት እና አዘጋጅ
3ኛ/ መድሃኒት ረዳ – የአዲስ ጉዳይ መጽሄት ሪፖርተር
በገዛ አገራችው መስራት ስላልቻሉ እናት አገራቸውን ኢትዮጵያን ለቀው ተሰደዋል። የወያኒው መንግስት ከምርጫ 2007 ቀደም ብሎ ነጻ ፕሬሶችን በማጥፈታ በራሱ አምሳል አዳዲስ ፕሬሶችን በመቅረጽ በ97 የደረሰበትን ሽንፈት አሁን እንዳይደርስበት በስፋት እየሰራ ሲሆን ሕዝብ የመረጃ ደሃ ለማድረግ በሚያደርገው ጥረት በዚህ አመት ብቻ ወደ 30 የሚጠጉ ጋዜጠኞች እንዲሰደዱ ሌሎችን ደሞ ወደ እስር ቤት እንዲገቡ አድርጓል።

re4

Minilik Salsawi (ምንሊክ ሳልሳዊ)

Viewing all 15006 articles
Browse latest View live