Quantcast
Channel: Ethiopian News | ዘ-ሐበሻ | Latest News Provider | News For All
Viewing all 15006 articles
Browse latest View live

አርበኞች ግንባር፣ ግንቦት 7 እና የአዲሃን ወደውህደት የሚያደርሳቸውን ውይይት ሊጀምሩ ነው

$
0
0

(ዘ-ሐበሻ) የኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባር፣ ግንቦት 7 የፍትህ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ እንዲሁም የአማራ ዲሞክራሲ ሃይሎች ንቅናቄ ወደ ውህደት የሚያደርሳቸውን ውይይት ሊጀምሩ መሆኑን ለዘ-ሐበሻ በላኩት መግለጫ አስታወቁ።

“የወያኔውን ዕድሜ ለማሳጠር በአንድነት እንሰራለን” በሚል ድርጅቶቹ በጋራ ባወጡት መግለጫ “ኢትዮጵያንና ሕዝቧን ካሉባት አዘቅት በማውጣት ሕዝቡ የስልጣን ባለቤት የሚሆንበትን ሁኔታ ለማመቻቸት የጋራ ትግልና መስዋዕትነት የግድ የሚለን ድረጃ መድረሳችንን የወያኔውን ቡድን ነፍጥ አንስተን እየተፋለምን ያለን ድርጅቶች ተጣንሪባ አንድ ሆኖ መታገል እንዳለብን ካመንን አመታትን አስቆጥረናል” ብለዋል።

ሙሉ መግለጫው የሚከተለው ነው፦

arbegnoch ginbar and ginbot 7


በጥፍሩም በጥርሱም ለስልጣን የሚተጋ መንግሰት …… እንዴት እንታገለው!!

$
0
0

ከግርማ ሰይፉ ማሩ

በጥፍሩም በጥርሱም ለስልጣኑ የሚተጋን መንግስት በሁሉን አቀፍ ትግል መጣል አለብን ብለው ጠብ መንጃ ቢያነሱ ክፋቱ ምን ላይ እንደሆነ አልታይህም እያለኝ ነው፡፡ ለምን በጠብ መንጃ ፍልሚያ ስልጣን መያዝ እንዳለብኝ በግሌ ባይገባኝም አሁን ግን የኢህአዴግ ዓይነት መንግሰት ከደርግ እንዴት እንደሚሻል ማሰብ እያቃተኝ ነው፡፡ የሰላማዊ ትግል ሰራዊት እንዴት እንገንባ ለሚለው ጥያቄ አፋጣኝ ምለሽ ካልሰጠን በስተቀር መንግሰት በግልፅ እየደገፈ ያለው በጠብ መንጃ ሊገዳደሩ የፈለጉት ነው፡፡ በሰላም ያልነውን ሰላም እየነሳን ይገኛል፡፡ መንግሰት ሆይ ሰላም እንድትሆን ሰላም ሰላም ለምንል ዜጎች ሰላም ሰጠን የምር የቀረበ ጥያቄ ነው፡፡

(ግርማ ሰይፉ)

(ግርማ ሰይፉ)


በፍትሕ አደባባይ የፈለገውን ማድረግ የወሰነ መንግሰት በእጅ አዙር ደግሞ በየማተሚያ ቤቱ እየሄደ መፅሄትና ጋዜጣ ታትሙና ወዮላችሁ ማለት ተያይዞታል፡፡ ይህ ከህግ ሰርዓት ውጭ በየማተሚያ ቤቱ በግንባር እና በስልክ የሚደረገው ማሰፈራሪያ ከወሮበላነት ውጭ ምንም ሊሆን አይችልም፡፡ መንግሰት ለህዝብ ጥቅም ሲባል ክስ መስርቻለሁ ብሎዋል፡፡ ህዝቡ የሚለው ግን ሌላ ነው፡፡ መፅሄት መቼ ነው የሚወጣው ነው፡፡ በቃ!!! ፍርድ ቤት በመፅሔትና ጋዜጦች ላይ ቢፊልግ እግድ ቢፈልግ ይዘጉ እሰኪል ድረስ ምን የሚያጣድፍ ነገር መጥቶ እንደሆነ ባናውቅም የመንግሰት አሽከሮች በየጉራንጉሩ ባሉ ማተሚያ ቤቶች ደጃፍ እየዞሩ ማሰፈራራት ተያይዘውታል፡፡ ሹሞቻችን ይህን አላደረግንም ብለው እንደሚክዱ ባውቅም ይህን ዓይነት ወሮበላነት ማስቆም ካልቻሉ ተጠያቂ እንደሚሆኑ መርሳት የለባቸውም፡፡ ስህተታችውን በአደባባይ ተችተን እንዲታረሙ የሚሰጣቸው ምክር ካንገሸገቸው የመጨረሻው ቀን ሲመጣ እንደሚጠየቁ ግን ማስታወስ ተገቢ ነው፡፡ የወሮበላ አለቃነት ከወሮበላነት በላይ የሚያስጠይቅ ነው፡፡ እነዚህን ወሮበላዎች አስቁሙልን ግልፅ አቤቱታ ነው፡፡ በየሳምንት ብዙ መቶ ሺ ብር ገቢ ያገኙ የነበሩ ማተሚያ ቤቶች በህጋዊ መስመር ሳይሆን በስልክና በቃል ከወሮበሎች በሚሰጥ ማሰፈራሪያ አጅ መስጠት እና ገበያ ማባረር ደግሞ የሚያስመሰግን ፍርሃት እንዳልሆነ ልብ ሊሉት ይገባል፡፡ የእያንዳንዳችን ፍርሃት ተደምሮ ነው እነርሱም ያለምንም ይሉኝታ ሊያሰፈራሩን ቤታቸውን ድረስ የሚመጡት፡፡ በወረቀት ትዕዛዝ ይድረሰኝ ለማለት ወኔ የሌለው ማተሚያ ቤት የሙት ዓመትና ተዝካር ወረቀት ሲያትም ይኖራታል፡፡

መንግሰት በሚዲያዎች ላይ በዶክመንተሪ ጀምሮት የነበረውን ወደ ፍትህ አደባባይ ያመጣውን የግል ሚዲያ አሁንም ገና አልበቃውም፡፡ በጥፍርም በጥርስም ሊዘለዝል እየባተተ ይገኛል፡፡ ኢትቪ ቤታችን ድረስ መጥቶ ለሆዳቸው ባደሩ ምሁራን ተብዬዎች እና ሹመኞች ሲሳደብ ያመሻል፡፡ የኮሚኒኬሸን ጉዳዮች መስሪያ ቤት ውስጥ ዳይሬክተር ናቸው የተባሉ ታምራት ደጀኔ የሚባሉ ኃላፊ መሰሪያ ቤቱ የመንግሰት ደሞዝ የሚከፈላቸው እኔ ጭምር በምከፍለው ግብር መሆኑን ዘንግተው የግል ፕሬስ ከተቃዋሚዎች ጋር ወግኖ እየሰራ ነው ብለው ከገዢው ፓርቲ ጎን ቆመው ሲከሱን አምሽተዋል፡፡ እኚህ ግለስብ ከተቃዋሚ ጎን መሰለፍ ማን ሀጥያት ነው እንዳላቸው አላውቅም፡፡ ተቃዋሚዎች በህግ ተመዝግበው የሚሰሩ ተቋማት እንደሆኑ እና የሚደግፋቸውም የሚቃወማቸውም ሰዎቸ መኖራቸው የሚጠበቅ መሆኑን ዘንግተውታል፡፡ ለነገሩ እርሳቸው የሚደግፉት ፓርቲ ነገ ተቃዋሚ የሚባል ወንበር ላይ ሊኖር እንደሚችል በተሰፋ ደረጃ ማሰብ አልቻሉም፡፡ ለነገሩ ኢህአዴግ በጥቅም የተገዙ አባላቶቹ ስልጣን ሲያጣ አብረውት እንደማይቆዩ ይረዳዋል- እርሳቸውንም ጨምሮ ማለቴ ነው፡፡ ለዚህም ነው ኢህአዴግ በጥርስም በጥፍርም ፍልሚያ ውስጥ የሚገባው፡፡ አቶ ታምራት ደጀኔ እንዲረዱ የምፈልገው የግሉ ፕሬስ ተቃዋሚን ቢደግፍ አንድም ነውር እንደሌለው ይልቁንም ገዢውን ፓርቲ ለመደገፍ ገዢው ፓርቲ ብቁ እንዳልሆነ ማሳያ ነው፡፡ ገዢው ፓርቲ በገንዘብ የሚደግፋቸው ነገር ግን ተደግፈው መቆም የማይችሉ “የግል” ተብዬ ሚዲያዎች እንደነበሩ መርሳት የለባቸውም፡፡ ለምሳሌ ኢፍቲን፣ ዛሚ፣ ወዘተ
ሰኞ ነሃሴ 19/2006 በቀረበው ዶክመንተሪ ተብዬ ዘባተሎ ላይ ከለየላቸው የመንግሰት ሹሞኞች እስከ ዩኒቨርሲት መምህራን አልፎ ተርፎም አትሌት ሀይሌ ገብረስላሴን ያሳተፈ ነበር፡፡ እርገጠኛ ነኝ ሀይሌ በሚዲያ ላይ ስለሚታዩ ግድፈቶች አጠቃላይ ሁኔታ ነበር የሚናገረው እንጂ አሁን ክስ ስለተመሰረተባቸው የግል ሚዲያዎች አልነበረም፡፡ ቆርጦ ቀጥሉ ኢቲቪ ግን ከህዝብ ጋር ሊያጋጨው ፍላጎቱን አሳይቶዋል፡፡ ሌላው ተዋናይ ዶክትረ አሸብር ወልደጊዮርጊስ ነበሩ፡፡ ከብዙ ጊዜ በተሻለ ሁኔታ ነበር መልስ አሰጣጣቸው፣ የከሰሱትም ሪፖርተርን ነው፡፡ መንግሰት ደግሞ ከሪፖርተር ጋር ጉዳይ የለውም፡፡ እንዲከሱ ሲጠበቅ የነበረው ሌላ ነበር፡፡ ይቅር ብያለሁ ብለው አልፈውታል፡፡ የእርሳቸው ይቅር ባይነት ከመንግሰት ሰፈር ሊገኝ አልቻለም፡፡ ተበቃይ መንግሰት ለስልጣኑ ሲል በጥፍሩም በጥርሱም ከግል ሚዲያው ጋር ግብ ግብ ገጥሞዋል፡፡ ማን ያሸንፋል አና መቼ ወደፊት የሚታይ ነው፡፡
የቀረበውን ዘጋቢ ፊልም ማስታወሻ ይዜ ለሁሉም በስማቸው አንፃር ለመፃፍ ነበር የፈለኩት ይህን ዘባተሎ የበዛበት ድሪቷም ዘጋቢ ተብዬ ከዚህ በላይ ማለት ተገቢ ሆኖ ስለአልተመቸኝ ተውኩት …. ይህ ዘጋቢ ፊልም ተብዬ የተሰራበት ሙሉ ዶክመንት ለታሪክ እንደሚቀር ተሰፋ አለኝ፡፡ የዛን ጊዜ እንወቃቀሳለን፡፡ ምሁራን ተብዬዎች በእናንተ ተሰፋ ቆርጠናል ….. በእናንተ መምህርነት አንድም የተሻለ ጋዜጠኛ እንደማናገኝ፡፡ ለነገሩ ልጆቹ የአስተማሪዎች ብቻ ሳይሆን የእኛም ናቸው እና በቤታችን ይማራሉ፡፡ ሀገር ማለት ልጄ ብለን እናስተምራለን፡፡

የበርማ የስደት መንግስት ለነጻነት ትግል አስኳል በመሆን የመራው የትግል ተሞክሮ

$
0
0

 

entc-logo-5የኢትዮጵያ ብሄራዊ የሽግግር ምክር ቤት ጁላይ 27 2014 ባወጣው መግለጫ፤ የወያኔን አፓርታይድ ስርዓት ለማስወገድና በሀሉ አቀፍ ህዝባዊ የሽግግር መንግስት ለመተካት ጥንስስ በመሆን መሰረት የሚጥልና የተበታተነውን ትግል በአንድነት ሊመራ የሚችል የአንድነት ሀይል (የስደት መንግስት እንደአማራጭ) እንዲቋቋም ሀገራዊ ጥሪ ማቅረቡ የሚታወስ ነው (ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ  http://goo.gl/KYP32s) ። ምክር ቤቱ ጥሪውን ተከትሎ ከሚመለከታቸው አካላትና ድርጅቶች ጋር የሁለትዮሽ ውይይት በማካሄድ ላይ ይገኛል። እስካሁን የተደረጉ ውይይቶች በአብዛኛው አበረታቶች ሲሆኑ አንዳንድ ወገኖች ደግሞ ምንም አይነት የተለየ አማራጭ ሳያቀርቡና የሌሎች አገራትን ተሞክሮ በጥልቅ ሳይፈትሹ አግዝፈው በመመልከት  አስቸጋሪና ሊተገበር የማይችል አድርገው ያምናሉ። የኢትዮጲያ ሕዝብ በሰቆቃ ውስጥ ሆኖ ፍዳውን በሚያይበትና ሀገራችን በመንታ መንገድ ላይ በምትገኝበት በዚህ ወሳኝ ወቅት እለታዊ ችግሮችን ከመተንተን ባለፈ የአማራጭ መፍትሔ በማቅረብና ስምምነት ላይ በመድረስ በአንድነት ትግሉን መምራትና ማካሄድ አማራጭ የሌለው ጉዳይ ሆኗል።

 

የአንድነት ሀይል (የስደት መንግስት እንደአማራጭ) የማቋቋም አስፈላጊነትን አስመልክቶ በተመሳሳይ ችግር ውስጥ የነበሩና በጨቋኝና አምባገነናዊ ስርዓቶች ተገፍተው ከአገር ውጭ የስደት መንግስት በማቋቋም ከታገሉና በትግል ላይ ካሉ የሌሎች ሀገራት ህዝቦች የትግል ሂደት በመመርመር ከተሞክሮው ግንዛቤ መውሰድ ለምናደርገው ትግል በጣም አስፈላጊ ነው። በተለይም ምርጫ 97ን ተከትሎ ወያኔ እያካሄደ ካለው የሰብዓዊ መብት ረገጣ፣ አፈና፤ እስር፤ ግድያ፤ በዘር ከፋፍሎ ማጋጨትና ዘረፋ ጋር በከፊልም ቢሆን ተመሳሳይ ታሪክ ያላት በርማ የምትባለውን አገር በምሳሌነት መውሰድ ጠቃሚ ነው።

 

በርማበደቡብምስራቅእስያየምትገኝበታይላንድናባንግላዴሽየምትዋሰንሀገርናት።በሲ.አይኤየመረጃሰነድመሰረትየበርማየቆዳስፋት 670ሺህካሬኪ/ሜትርይገመታል።ይህማለትየኢትዮጵያግማሽያህልስፋትአላትማለትነው።የህዝቧብዛትምወደ 56 ሚሊዮንይገመታል።በርማበጃፓንቅኝአገዛዝስርየነበረችሲሆንበ1948 ዓ.ምእ.ኤ.አበእንግሊዝእርዳታነጻነቷንአግኝታለች።

በ1962 ዓ.ምእ.ኤ.አጄኔራልነዊንየተሰኙየሰራዊቱአዛዥበመፈንቅለመንግስትስልጣንተቆጣጥረውበሀገሪቱላይየወታደራዊጁንታይመሰርታሉ።ህዝቡንናሀገሪቱንበፍጹምየጭቆናቀንበርውስጥበማስገባታቸውበአለምደረጃበሰብአዊመብትረገጣበቀደምትነትከተመዘገቡትሀገራትውስጥበርማለመገኘትበቃች።ጁንታውየዲሞክራሲሀይሎችንሙሉለሙሉከሀገሪቷአጥፍቶየበርማሶሻሊስትፕሮግራምተብሎየሚጠራው  የአንድፓርቲአምባገነናዊአስተዳደርንአሰፈነ።

ሀገሪቷ ከጎርቤት ሀገራትና ከሌሎች የአለም ሀገራት የተገለለች ብቸኛ እንድትሆን በማድረጉ በአለም ድሀ ከሚባሉት ሀገራት ተርታ እንድትሰለፍ ከፍተኛ አስተዋጽኦ አድርጓል። በመንግስት ባለስልጣናት የሚደረገው ዘረፋና የአስተዳደር ብልሹነት በሩዝ ምርት አቅራቢነት ትጠቀስ የነበርችውን የበርማን ኢኮኖሚ አሽመድምዶ ህዝቡን የድህነት ማቅ አለበሰው። የህዝቡ ችግር ከሚሸከመው በላይ በመድረሱ በ1987 ዓ.ም እ.ኤ.አ የበርማ ህዝብ መሪዎቹን በመቃወም በሕዛባዊ እምቢተኝነት ወደ አደባባይ ተመመ።

 

በህዝብ የተቀሰቀሰው አብዮት ምንም እንኳን ለብዙ ሺህ በርማውያን ህይወት መጥፋት ምክንያት ቢሆንም አመጹ እያየለ መጥቶ በ1988 ዓ.ም ፈላጭ ቆራጩ የወታደራዊ ጁንታ ጄኔራል ዊን ከስልጣን ለቀቁ። በህዝባዊ ማእበልና በዘር ፖለቲካ የተናጠችውን ሀገር በማረጋጋት ሰበብ  የወታደሩ ክፍል ስልጣኑን ሳይለቅ፤ የመድበለ ፓርቲ ዲሞክራሲ በመፍቀድ ነጻና ህዝባዊ ምርጫ ለማደረግ ቃል በመግባትና በማዘናጋት አመጹን በተወሰነ መልኩ ለጊዜው አረጋጋው።

በዚህ መሰረት መሰረት በ1990 ዓ.ም እ.ኤ.አ በበርማ ታሪክ የመጀመርያውን ነጻ ምርጫ ለመካሄድ በቃ። በአጭር ጊዜ ተደራጅተው የወታደራዊውን ገዥ ፓርቲ በምርጫ ከገጠሙት በርካታ የተቃዋሚ የፖለቲካ ድርጅቶች ውስጥ አንዱ የብሄራዊ ዲሞክራሲያዊ ሊግ (National League for Democracy) በመባል የሚታወቀው በከፍተኛ የህዝብ ድጋፍ በምርጫ አሸናፊ መሆኑ ተረጋገጠ።

በሃገራችን ምርጫ 97ን ተከትሎ ወያኔ እንዳካሄደው ድርጊት፤ የበርማም ወታደራዊ ጁንታም በግፍ የመግዛት ጥም ገና ያልወጣለት የአምባገነኖች ስብስብ በመሆኑ ውጤቱን በጸጋ ሊቀበለው ፈቃደኛ አልሆነም። የህዝብ ድምጽ መነጠቁን ተከትሎ በተነሳው ህዝባዊ ቁጣ ብዙ የበርማ ዜጎች ህይወት በጨካኙ አምባገነናዊ አገዛዝ የጥይት እራት ሆኑ። ቁጥራቸው በርካታ የሆኑ የተቃዋሚ ድርጅት አመራሮች እየታደኑ ወደ ወህኒ እንዲወርዱ ተደረገ። ገሚሱም ወደየጎርቤት ሀገራት ተሰደደ። የአሸናፊው ፓርቲ የብሄራዊ ዲሞክራሲያዊ ሊግ (National League for Democracy – NLD) መሪና የኖቤል ተሸላሚ የሆኑት ወ/ሮ አን ሳን ሱቺ ከሰው ጋር እንዳይገናኙና በቁም እስር እንዲቆዩ ተደረገ።

ይህንን አይን ያወጣ የህዝብ ድምጽ ንጥቂያ አንቀበልም በማለት ከእስርና ጭፍጨፋው ማእበል ተርፈው ወደ ጎረቤት ሀገር የተሰደዱት የተቃዋሚ ፖለቲካ መሪዎች በበርማና በታይላንድ የድንበር ከተማ ላይ National Coalition Government Union of Burma (NCGUB) በሚል ስም በስደት የሚንቀሳቀስ መንግስት አቋቋሙ። የተቋቋመው ይህ የስደት መንግስት የአን ሳን ሱቺን NLD ፓርቲ ጨምሮ በርካታ ተቃዋሚ ሀይሎችን ያቀፈ ነበር።

ይህ የበርማ የስደት መንግስት መቀመጫውን በዩናይትድ ስቴትስ አሜሪካ በማድረግና ለበርማ የነጻነት ትግል አስኳል በመሆን በተከታዮቹ አመታት የተለያዩ እንቅስቃሴዎችን መርቷል። የስደት መንግስቱ የተቃዋሚዎችን ድምጽና ትግል አንድ አድርጎ የፖለቲካና የዲፕሎማሲ ትግሉን ሲመራና ሲያስተባብር ቆይቷል። በአለም መንግስታትም ከበሬታን እያገኘ በመሄዱ፤ የተለያዩ ሀገር ባለስልጣናትን በማነጋገርና ከፍተኛ የዲፕሎማሲ ስራዎችን በመስራት በበርማው ጨቋኝ ስርዓት ላይ ከፍተኛ ተፅእኖ ለማስደረግ ችሏል።

በዶ/ር ሴይን ዊን የሚመራው የበርማ የስደት መንግስት በተለያየ ጊዜ ከአሜሪካና ከአውሮፓ የህግ መወሰኛ ምክር ቤት ተወካዮች ጋር ውይይት በማድረግ በሀገሪቱ ጉዳይ ላይ ተጨባጭ የሆኑ ስራዎችን ሰርቷል። በበርማ የነጻነት ትግል ውስጥ በዲፕሎማሲ በኩል ካደረጋቸው አስተዋፅኦዎች ውስጥ፤

በ 1997 ዓ.ም እ አኤአ የአሜሪካው የህግ መወሰኛ ምክር ቤት የኮሄን-ፋይንስታይን ማሻሻያ Cohen-Fienstein Amendment-Section 569 of the Foreign Operations and Appropriations Act በበርማ መንግስትና በባለስልጣናቱ ላይ ከፍተኛ የኢኮኖሚና የመንቀሳቀስ መብትን የሚገድብ እቀባ ህግ እንዲፀድቅ ትግል አድርጓል።

ለተባበሩት መንግስታት አባል ሀገራት የበርማን ፖለቲካ ቀውስ ሳይታክት በማስገንዘብ፤ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የበርማን ህዝብ ሰብአዊ መብትና ነጻነት መከበር የሚጠይቁ ውሳኔዎችን (resolutions) እንዲያፀድቅ ከፍተኛ ትግል አድርጓል።  UN RESOLUTIONS A/RES/47/144, A/RES/48/150, A/RES/49/197,etc

የስደት መንግስቱ ከውጭ ትግሉን ሲያካሂድና ግፊቱን ሲያደርግ ከውስጥም ከውጭም ያለው ግፊት በመጠንከሩ በ2010 ዓ.ም የወታደራዊው መንግስት በድጋሚ ህዝባዊ ምርጫ ለማካሄድ ተገደደ። በተለመደው የአምባገነኖች ታክቲክ በምርጫው የተቃዋሚ ሀይሎች ተመጣጣኝ የመጫወቻ ሜዳ ካለማግኘታቸውም በላይ ምርጫው ግልጽና ፍትሐዊ ያልነበረ በመሆኑ ብዙዎቹ ድርጅቶች እራሳቸውን ያገለሉ አለበለዚያም ለይስሙላ የተወዳደሩ ነበሩ።

 

ምንም እንኳን ገዥው ፓርቲ ምርጫውን በመንጠቅ በጉልበት አሸናፊነቱን ቢያውጅም የትግሉን አቅጣጫ ሊያስቀይረው ባለመቻሉ የተቃዋሚ ሀይሎች በአንጻራዊ ነጻነት መንቀሳቀስ እንዲችሉ ሁኔታዎች እንዲመቻቹላቸው ተደረገ። የተቃዋሚ ፓርቲ አመራር አባላት አን ሳን ሱቺን ጨምሮ ከሞላ ጎደል በነጻነት በመንቀሳቀስ በ 2012 ዓ.ም ምርጫ በሀገሪቱ ከሚገኙት ከተሞች በዋና ዋናዎቹ ላይ ተወዳድረው በአሸናፊነት ወደ ፓርላማ ገብተዋል። ሌሎች የተቃዋሚ ድርጅት አመራሮችም በአሁኑ ሰአት ወደ አገራቸው ተመልሰው በመታገል ላይ ይገኛሉ።

ሀገሪቱ ውስጥ እይታየ ያለውን የፖለቲካ ለውጥ ከግምት ውስጥ በማስገባት፤ ለነጻነት ሲንቀሳቀስ የነበረው የስደት መንግስት በ September 2012 ዓ.ም እራሱን ማክሰሙን (dissolve) አስታውቋል። አባል ድርጅቶቹም ወደ ሀገራቸው ተመልሰው በፖለቲካው ለመሳተፍ የበኩላቸውን እያደረጉ ነው። ምንም እንኳን የሀገርቱ ችግር ገና ብዙ የሚቀረው ቢሆንም በተሻለ ጉዞ ላይ ትገኛለች።

አገራችን ኢትዮጵያ በወያኔ ያፓረታይድ  ስርዓት ስር እየማቀቀች በምትገኝበት በዚህ ወሳኝ ወቅት። ተቃዋሚ ሀይሎች በየፊናችን የምናደርገው ሩጫ ወደለውጥ መንገድ ሊመራን ካለመቻሉም አልፎ፤ የኢትዮጵያን ህዝብ ግራ በማጋባትና ተስፋ በማስቆረጥ ለጨቋኙ የወያኔ መንግስት የተመቸ ሁኔታ ፈጥሮለታል። ለዘመናት ተመሳሳይ ነገሮችን በማድረግ የተለየ ውጤት ከመጠበቅ አባዜ በመውጣት ለየት ያሉ አማራጮችን መቀበል ወይም ማቅረብ አራሱን የቻለ የፖለቲካ ጥበብ መሆኑን በመገንዘብና ልዩነታችንን በማጥበብ ከላይ ባጭሩ ለምሳሌነት የቀረበውን የበርማ ህዝብ የትግል ታሪክና የሌሎችንም ተሞክሮ በምሳሌነት በመውሰድ ኢትዮጲያዊነትን መሰረት ያደረገ አንድ ወጥ አመራር ያለው የተባበረ ሀይል (የስደት መንግስት እንደ አማራጭ)  በማቋቋም ስርአቱን ማስወገድ ወይም ማስገደድ የወቀቱ አንገብጋቢ ጥያቄ ነው።

 

ትግሉንና ድሉን የጋራ እምናደርገው፤ ዘላቂ መፍትሄ ሊያመጣ የሚችል ያንድነትና የአማራጭ ሃይል ነጥሮ ሲወጣ በመሆኑ ዛሬም እንደወትሮው ለሀገር ወዳድና ነጻነት ናፋቂ ወገኖችኖች፤ እንዲሁም ለመገናኛ ብዙሃን ተቋማት በዚህ ዙሪያ አስፈላጊውን ሁሉ እንድታደርጉ ሃገራዊ ጥሪያችንን እናቀርባለን። በተመሳሳይ የተለያዩ ድርጅቶች አሉኝ የሚሏቸዉን የአማራጭ መፍትሄዎችን ለህዝብ ለውይይት ይፋ እንዲያደርጉ እንጋብዛለን።

 

የኢትዮጵያ በሔራዊ የሽግግር ምክር ቤት በመርህ ደረጃ የወያኔ/ኢሕአደግ ስርአትን ማስወገድ መተካት የማይነጣጠሉ የአንድ ሳንቲም ገጽታዎች እንደሁኑ በጽኑ ያምናል። ይህንን ጭብጥ በተመለከተ ለመቋጫ ይረዳ ዘንድ  በሃገር ውስጥ ከሚገኙ የፖለቲካ ድረጅት መሪዎች ከተናገሩት ለናሙና ይህንን በመጫን ያድምጡ http://goo.gl/S2g7Ep

 

 

ትግሉንና ድሉን የጋራ እናድርገው!

 

የኢትዮጵያ ብሔራዊ የሽግግር ምክር ቤት

“የፀረ ሽብር ህጉ ሰለባዎች”–ሊያዩት የሚገባ አዲስ ዶክመንታሪ ፊልም (ይዘነዋል)

$
0
0

የፍኖተ ነፃነት ዝግጅት ክፍል “የጸረ ሽብር ህጉ ስለባዎች” የሚል አዲስ ዶክመንታሪ ፊልም ሰርቶ ለቋል። 43 ደቂቃ የሚፈጀውን ይህን ዶክመንታሪ ይመልከቱት።

“የፀረ ሽብር ህጉ ሰለባዎች”  – ሊያዩት የሚገባ ዶክመንታሪ ፊልም (ይዘነዋል)

የአቶ ገብሩ አስራት አዲስ መጽሐፍ በዋሽንግተን ዲሲ እንደሚመረቅ ታወቀ

$
0
0

ኢየሩሳሌም አረአያ እንደዘገበችው፦

የቀድሞ የትግራይ ፕሬዝዳንትና የሕወሐት/ኢህአዴግ ከፍተኛ አመራር አባል የነበሩትና በ1993ዓ.ም ከአቶ መለስ ዜናዊ ጋር በፈጠሩት የፖለቲካ ልዩነት ከስልጣናቸው እንዲባረሩ ከተደረጉት መካከል አንዱ የሆኑት አቶ ገብሩ አስራት 516 ገፅ የሸፈነ መፅሐፍ ማዘጋጀታቸው ታውቋል።

«ሉአላዊነትና ዴሞክራሲ በኢትዮጵያ» የሚል ርዕስ የተሰጠው ይኸው መፅሐፍ የድርጅቱን አጠቃላይ ጉዞ የሚፈትሽና ሕዝብ ዘንድ ያልደረሱ በርካታ መረጃዎችን ያካተተ እንደሆነ ተመልክቷል። መፅሐፉ ከሴፕቴምበር 1 ቀን 2014 ዓ.ም ጀምሮ ለገበያ እንደሚውል ሲታወቅ በዚሁ ዕለት በዋሽንግተን ዲሲ የምረቃ ስነስርአት እንደተዘጋጀ ማወቅ ተችሏል። አቶ ገብሩ በ1997ዓ.ም መስቀል አደባባይ በተጠራ የተቃውሞ ሰልፍ በይፋ ህዝብን ይቅርታ ከመጠየቃቸውም ባሻገር በስልጣን ላይ እያሉ ለተፈፀመ ጥፋት አብረው እንደሚጠየቁ መናገራቸው ይታወሳል። «ቤሳ ቤስቲን እንደሌለው አውቃለሁ» ሲሉ አቶ መለስ ዜናዊ በ1994ዓ.ም ስለአቶ ገብሩ አስራት ንፁህነት መናገራቸው አይዘነጋም።

Gebru asrat

ያልተገራውን ስርዓት የማዳን ርብርብ

$
0
0

ከጌታቸው ሺፈራው

ህወሓት/ኢህአዴግ ስልጣን ከያዘበት ጊዜ ጀምሮ እንደ ደቡብ አፍሪካ ያሉ አገራት ነጻነታቸውን አግኝተው የዓለም ቀጣይ ኃያል አገራትን ተቀላቅለዋል፡፡ አብዛኛው የዓለም ማህበረሰብ ዴሞክራሲያዊ በሆኑ ስርዓቶች ለመተዳደር እድል አግኝቷል፡፡ ህወሓት/ኢህአዴግ ግን ስልጣን ከያዘ ማግስት በህግ ፈቀድኩት ያለውን የሚዲያ ነጻነትን ጨምሮ በማፈን፣ በዛው በርሃ ውስጥ በነበረው ‹‹ውርጋጥነቱ›› ቀጥሏል፡፡ አሁንም ቢሆን ‹‹ሲቪል›› ነኝ ብሎ የሚያስበው በአፈሙዝ ነው፡፡ በአንድ በኩል ዴሞክራትነቱን እያስወራ በተግባር ግን የአምባገነኖች ቁንጮ ሆኖ ቀጥሏል፡፡ በአጠቃላይ በርሃ ከነበረበትም በባሰ አሁንም እንዳፈተተው በኢትዮጵያውያን ላይ ስልጣኑን የሚያስጠብቅለትን እርምጃ መውሰዱን ቀጥሏል፡፡ ኢህአዴግ አልተገራም፡፡
Haile
እንዲያም ሆኖ ግን ሌሎቹን ስለ መግራት ያወራል፡፡ ትናንትና ማታ (ነሐሴ 19/2006) በልሳኑ ያሳየው ‹‹ያልተገሩ ብዕሮች›› የተሰኘ ፊልም የሚያሳየውም ይህንን ከአለ-አቅም መንጠራራትን ነው፡፡ ኃይሌና ገና በጋዜጠኝነት ተመረቁ የተባሉ ወጣቶች የእነ ፕሮፌሰር መስፍንን፣ የእነ ዶክተር በድሉ ዋቅጅራን፣ የእነ ተመስገን ደሳለኝን፣ የእነ ዓለማየሁ ገላጋይን ብዕር ‹‹ሊገሩ›› ሲፍጨረጨሩ ማየት በእጅጉ የሚያስገርም ነው፡፡

ሲያሸንፍም በስሜት የዘለልንለት፣ ሲሸነፍ የተሸነፍንለት የድሮው አትሌት ኃይሌ ገብረስላሴ ከስርዓቱ ጋር አብሮ ‹‹ሚዲያ ኑክሊየር ነው!›› ሲል ‹‹አጥፊነቱን›› መስክሯል፡፡ በእርግጥ ኃይሌ በህዝብ ላይ ሲቀልድ ይህ የመጀመሪያው አይደለም፡፡ ከአመት በፊት በሰይፉ ፋንታሁን የሬዲዮ ፕሮግራም ላይ ስለ መምህራን የደሞዝ ጭማሬ ተጠይቆ የመምህራኖቹ የደምወዝ ጭማሬ ቅብጠት መሆኑን ተናግሯል፡፡ ከአንድ አስተማማኝ የመረጃ ምንጭ እንዳገኘሁት ከሆነ ኃይሌ ገብረስላሴ ለስርዓቱ አፋኝነትም በግልጽ ድጋፉን እያሳየ እንደሚገኝ ነው፡፡ የመረጃ ምንጩ እንደጠቀሰልኝ የተቃዋሚ ፓርቲ አባላት የሚታጎሩበት የካ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያ ማስፋፊያ የተሰራው በኃይሌ ገብረስላሴ የገንዘብ እገዛ ነው፡፡ ለዚህ ፖሊስ ጣቢያ ካቴና ከውጭ አገር ያስመጣውም ኃይሌ ገብረስላሴ እንደሆነ ምንጩ ገልጾልኛል፡፡

በርካታ ኢንቨስትመንቶቹ በገዥው ፓርቲ ይሁንታ እንደሚቀጥሉ ያመነ የመሰለው ኃይሌ ትናንትናውም ቢሆን የስርዓቱ መሳሪያ ሆኖ ሚዲያውን ሲተች ያመሸው ከራሱ የኢኮኖሚ ጥቅም አንጻር ነው፡፡ ኃይሌ ከኑክሊየርም በላይ አፍራሽ ነው ያለውን ሚዲያ መተቸት የጀመረው በአንድ ዘገባ ምክንያት አንድ የውሃ ፋብሪካ መዘጋቱን በመግለጽ ነው፡፡ ኃይሌ ይህን ወደ ራሱ አስጠግቶ ሲያጠናክርም ‹‹በእኔ ላይ በመጻፉ ልጆቼ፣ ቤተሰቤ ያያሉ፡፡ በስሬ 1500 ሰራተኛ አለ፡፡ አዋሳ፣ ባህርዳር፣…ያሉት ሰራተኞችም ያዩታል፡፡ ሰራተኞችም ይህ ሰው ምን ነካው ይላሉ፡፡ ቢዝነስ ‹ኮላፕስ› ያደርጋል፡፡›› ሲል ነበር የገለጸው፡፡ እንግዲህ ገና የኃይሌ ልጅ ትሰማለች ተብሎ፣ ሰራተኞቹ ‹‹ምን ነካው!›› ስለሚሉ፣ ‹‹ቢዝነሱ ኮላፕስ›› ስለሚያደርግ ኃይሌ ምንም ያህል ቢያጠፋ ሚዲያው ትንፍሽ ላይል ነው ማለት ነው፡፡ ይህን የኃይሌን ሀሳብ የጋዜጠኝነት ትምህርት ቤት ውስጥ መምህር ነች የተባለችውም ‹‹የሰዎች ጓዳ (መቼስ ሚስጥር ማለቷ ነው) ሚዲያ ላይ መውጣት የለበትም፡፡›› ስትል ሀሳባቸውን ተሰብስበው የተስማሙበት አስመስላዋለች፡፡ በቃ ሚዲያ ሚስጥር የማውጣት ሚናውን በእነ ኃይሌ ዳኝነት ተቀማ ማለት ነው፡፡ እነ ኃይሌና ዶክተር አሸብር ለስርዓቱ ክንድ በሆኑበት በዛው ፊልም ላይ ካሳ ተከፍሏቸዋል፡፡ ለዚህም ነው ‹‹ኃይሌ ገብረስላሴ ሊወዳደር ነው፣ ዶ/ር አሸብር አምባገነን ነው›› የሚሉ ዜናዎችና ትችቶች ሳይቀር በአጥፊነት የተፈረጁላቸው፡፡

ሚዲያ ከሌለው መንግስት ይልቅ መንግስት የሌለው ሚዲያ ይሻላል የሚል መርህ የሚከተሉትን የእንግሊዝና የአሜሪካን ዴሞክራሲ አውቀዋለሁ ያለው ኃይሌ ገብረስላሴ ‹‹ጦር ከፈታው ወሬ የፈታው›› በሚል ኢትዮጵያ ውስጥ ያለው ሚዲያ ‹‹ያልተገራ›› በመሆኑ በሚያሳስብ መልኩ ያ ስቅስቅ ብሎ ያለቀሰለትን ጠቅላይ ሚኒስትር ‹‹ራዕይ›› እናስጠብቃለን የሚሉ አካላት እርምጃ እንዲወስዱ ፍርደ-ገምድልነቱን አሳይቷል፡፡

ስርዓቱን የማዳን እርብርብ

በዚህ ፊልም ላይ ስለ ሰራዊት ፍቅሬ የፍቅር ደብዳቤ መጻፍ፣ በሞቅታ ስለሚጨፍሩት አርቲስቶች አስተያየት መስጠት በአውዳሚነት አስፈርጇል፡፡ ይህ የሆነው እነዚህ ‹‹ልማታዊ አርቲስቶች›› ያልተገራው ስርዓቱ ቅቡልነት እንዲያገኝ ሳይታክቱ የሚሰሩ በመሆናቸው ነው፡፡ ከዚህ በተጨማሪ ‹‹አባይ ለፕሮፖጋንዳ አይዋል›› ማለት ብሄራዊ ደህንነትን ተጻርሮ የቆመ አስመስሏል፡፡ ከምንም በላይ ስርዓቱ ለስልጣኑ መሰረት አድርጎ የሚወስዳቸው አንጓዎች በሚዲያው ሊነኩ የማይገባ ‹‹ቀይ መስመሮች›› ተደርገው ማስጠንቀቂያ ተሰጥቶባቸዋል፡፡ መቼም አንድ ተቃዋሚ መንግስትን የተቆጣጠረውን ፓርቲ ከስልጣን አውርዶ መንግስት ለመሆነ ነው የሚሰራው፡፡ ያልተገራው ‹‹መንግስት›› መሳሪያ የሆኑትና እነሱም ከስርዓቱ ጋር በጥቅም ከመጋራታቸው ውጭ የተገራ ነገር ያልታየባቸው ነገር ግን የተገሩትን ሲያጣምሙ የታዩት የፊልሙ ሰሪዎች ግን ‹‹ህዝብ ሌላ መንግስት ለማየት ፍላጎት አለው›› የሚለውን ከኑክሊየርም በላይ አጥፊ ነው ብለው ፈርጀውታል፡፡ ጋዜጠኝነት ‹‹በራዲካል ሮል›› ፖሊሲ የማስቀየር ሚና አለው ብለው ሳይጨርሱ ‹‹የብሄር ፌደራሊዝሙ እርምት ያስፈልገዋል›› የሚልን መካሪ ጽሁፍ በአሉታዊነት ለፈውታል፡፡ የ‹‹ብሄር ፖለቲካው›› ላይ ምንም አይነት ትችት መቅረብ የለበትም አይነት ያልተገራ አቋማቸውን ዳግመኛ አሳይተውበታል፡፡ ጠባብ አለመሆናቸውን ማሳመን ሲያቅታቸው ጠባብነታቸውን የሚተቹትን ሚዲያዎች ያልተገሩ ሲሉ ወርፈዋቸዋል፡፡ እነሱ አንዳንድ ተቋማት ስለ ‹‹መንግስት›› ያወጧቸውን መልካም የሚባሉ ነገሮች አመት ሙሉ እንደማይደጋግሙ ዓለም አቀፍ ተቋማት ስለ ድህነት፣ የመፈንቅለ መንግስት ስጋትና ሌሎችም ጉዳዮች ላይ ያወጧቸውን ሪፖርቶች የግል ሚዲያው እንዳያወጣ ቅድመ ክልከላ አውጀዋል፡፡ ማጎሪያ ቤት ውስጥ ያለውን ስቃይ ማስተባበል ሲያቅታቸው ‹‹ማረሚያ የሚያስፈልገው ማረሚያ ቤት›› የተሰኘን መካሪ ጽሁፍ በህገ ወጥነት ፈርጀውታል፡፡

Dr asheber pimping for his own presidency (Video)ኢህአዴግ የውድቀት ዋዜማ፣ ኢትዮጵያ ለምን አሚሶንን ተቀላቀለች? ፍትህ በሌለበት የፍትህ ሳምንት፣ ለአክራሪነት አስተማሪው ማን ነው? ለተሰኙት መልስ መስጠት ሲያቅታቸው፣ እውነት ሆኖ እንቅልፍ ሲነሳቸው በጸረ ሽብር ህጉ አውድ አሸባሪ ብለው ፈርጀዋቸዋል፡፡ በጣም የሚገርመው አብዛኛዎቹ ጽሁፎች በጥያቄ የቀረቡና ኢህአዴግን ብቻ ሳይሆን የተለያዩ አካላትን ተጠያቂ የሚያደርጉ ሲሆኑ ኢህአዴግ ግን ቀድሞ ‹‹እኔን ነው›› ብሎ ለራሱ ወስዷቸዋል፡፡ ሚዲያው ገለልተኝነቱን እያሳየም ቢሆን እነሱ የአንድ አካል አፈ ቀላጤ ይሉታል፡፡ ለዚህ እንደ ማስረጃ ያቀረቡት ደግሞ ‹‹ማንን እንመን?›› በሚል የወጣን አንድ ጽሁፍ ነው፡፡ ይህ ጽሁፍ ዶ/ር ብርሃኑንና በረከት ስምዖንን ያፋጠጠ ጽሁፍ ነው፡፡ ከሁለቱ አካላት ማንንን እንመን ተብሎ በማነጻጸሪያነት የወጣውን ይህን ጽሁፍ ራሱን የማያምነው ኢህአዴግ ‹‹እኔን ነው የማያምኑኝ›› ብሎ ጥፋቱን ቀድሞ ወስዶ ‹‹የአንድ አካል አፈቀላጤ ሆነዋል›› ሲል ይከሳል፡፡

በአጠቃላይ ‹‹ያልተገሩ ብዕሮች›› በሚል የቀረበው ፊልም የኢህአዴግን ፖሊሲ መተቸት ህገ ወጥነት እንደሆነ የታየበት፣ የስርዓቱ ዋና ዋና የስልጣን ማቆያ ፖሊሲዎችን መንካት ስርዓቱን ሊያፈራርሰው እንደሚችል ባልተገራ አንደበት የተነገረበት ፊልም ነው፡፡ በፊልሙ ተዋናይ የሆኑት አካላት እዛው ፊልሙ ላይ ‹‹ፌቨር›› እየተሰራላቸው በትውልዱ ላይ ሲፈርዱ ስርዓቱን ለማዳን እርብርብ ላይ እንደሆኑ በግልጽ ለማየት ተችሏል፡፡ ሁሉንም ነገር ከኢኮኖሚ አንጻር ሲቃኝ ያመሸው አትሌት ኃይሌ ገብረስላሴ ‹‹ጦርነት ከፈታው ወሬ የፈታው›› በሚል ኃይል በእጁ ለሆነው ያልተገራ ስርዓት በቅኔ እርምጃ እንዲወስድ አሳስቧል፡፡ የስፖርት ጋዜጦች ድረስ ተሂዶ የተደረጉበት ጥቃቅን ትችቶች በህገ ወጥነት የተፈረጁለት ዶክተር አሸብር በግልጽ አገልጋይነቱንና ስርዓቱን ለማዳን የቆመ መሆኑን አሳይቷል፡፡ ፓርላማ ላይ ኢትዮጵያ ምንም አይነት ጥቅም ሳታገኝ ለጅቡቲ ውሃ የሚለግሰውን አዋጅ ከተቃወሙት መካከል ዶክተሩ አንዱ እንደነበሩ በሚዲያ ተገልጾ የነበር ቢሆንም ዶክተሩ ግን ስለ አዋጁ ያላቸውን ይሁንታ ሲገልጹ ‹‹ከእኛ ጋር ሳይደርስ ለምን አይጸድቅም?›› የሚል ጥያቄ አቅርበው እንደነበር ገልጸዋል፡፡ የህዝብ ተወካይ ነኝ ብሎ አንድን ህግ ‹‹ፓርላማ ሳይመጣ ለምን ራሱ ኢህአዴግ አያጸድቀውም›› ማለት ስርዓቱን ለማዳን እርብርብ ላይ መሆናቸውን የሚያሳይ ነው፡፡

በአጠቃላይ በፊልሙ ላይ በአሉታዊነት የተፈረጁት ጽሁፎች ቢበዛ መካሪ ቢሆኑ እንጂ ይህ ነው የሚባል ‹‹አለመገራት›› አይታይባቸውም፡፡ ነገር ግን ባለመገራቱ ሳይነካ የሚደነብረውን ስርዓት ይበልጡን የሚያስበረግጉ መሆናቸው የሚያስገርም አይሆንም፡፡
እነ ኃይሌ ዴሞክራሲን አይቼባቸዋለሁ ባሏቸው አገራት ሚዲያ አራተኛ የመንግስት አካል ቢሆንም ኢትዮጵያ ውስጥ ሶስቱ የመንግስት አካላትም ሆነ መንግስት ባለመኖሩ አራተኛ መንግስት ሊሆን አልቻለም፡፡ ከዚህ ይልቅ መንግስት በሌለበት፣ ካልተገራ ዘመናዊ የቤተ መንግስት ወንበዴ ጋር ግብ ግብ የሚገጥም ብቸኛው የመንግስት አካል ሆኖ ለማገልገል ጥረት ሲያደርግ ቆይቷል፡፡ ይህ ደግሞ መንግስትም ሆነ የመንግስት አካላት እንዳይኖሩ የሚፈልገውንና ልጥ ሲያይ እባብ ነው ብሎ የሚደነብር ያልተገራ ስርዓት እጅጉን አስደንብሮታል፡፡ ስለ ተገራና ስላልተገራ ብዕር ይህ ነው የሚባል እውቀት የሌላቸው፣ የማያገባቸው እነ ኃይሌም ያልተገራው ስርዓት ጋር የተጋሩትን ጥቅም ለማስጠበቅ ሲሉ ስርዓቱ በሚዲያው ላይ እርግጫውን በመሰንዘር እራሱን እንዲያድን እርብርብ አድርገዋል፡፡ የእነ ኃይሌ ምክር ስርዓቱ እንደለመደው እንዲራገጥ የሚገፋፋ ቢሆንም ማዳን አለማዳኑንም ሆነ እነሱ በትውልዱ ላይ እየፈጸሙት ያለውን በደል ግን ታሪክ የሚፈርደው ይሆናል፡፡

የማለዳ ወግ …የኢቲቪ ”ያልተገሩ ብዕሮች ”ዘጋቢ ፊልምና ያልተገራው አቀራረብ ….

$
0
0

ነብዪ ሲራክ ከሳዑዲ አረቢያ

ከሁለት ሰአቱ የኢቲቪ ዜና አወጃ ተከትሎ የቀረበውን ” ያልተገሩ ብዕሮች ” ዶክመንተሪ በደረቁ ሌሊት ድጋሜ ስርጭቱ ተከታትየ ጨረስኩት … ላፍታ እንደተጠናቀቀ ዝም ፣ ጭጭ አልኩና በሃሳቤ በህዝብ ገንዘብ ከፍተኛ ወጭ እየተደረገባቸው የሚሰራጩትን የመንግስት የህትመት ጽሁፍና የኤሌክትሮኒክስ መገናኛ ብዙሃንን አሰብኳቸው … በምናብ ብዙ ርቄ ሔጀ በዶደመ ፣ ባልተገራ እና በተባውና በተገራው ብዕር ውስጥ ራሴን አትኩሮት ሰጥቸ የመገናኛ ብዙሃን ውጤቶች በሃሳብ ተመላለስኩባች ! ሰፊ ሽፋን ያለውን ኢቲቪና ራዲዮኑን ፣ በየቀኑ እየታተሙ የሚወጡትን እነ አዲስ ዘመንን ጋዜጣንና የመሳሰሉት እሰብኳቸው …አስቤ አሰላስየ ወደ ደረስኩበት ድምዳሜ ከማቅናቴ በፊት ግን በ”ያልተገሩ ብዕሮች ” ዘጋቢ ፊልም ዙሪያ የታዘብኩትን ቀዳሚ አድርጌ የተሰማኝን ላካፍልዎ ወድጃለሁ…
haile Gebresilase
” ያልተገሩ ብዕሮች ” …

…ስለ ጋዜጠኝነት ስነ ምግባር ከባለ ሙያዎች የቀረበው መግለጫ ዘጋቢ ፊልሙ የተነሳበትን አላማ በሚያሳካ መልኩ የተጠናቀረ ስለሚሸት ፣ ስለሚመስል አልተመቸኝም። ከሙያው ጋር ግንኙነት የሌላቸው ወገኖች የሰጡት አስተያየት የግል አመለካከታቸው ነውና ብዘለውም ባዕድ በሆኑት ሙያ የሰጡት ግምገማ አልተዋጠልኝም። “ፍየል ወዲህ ቅዝምዝም ወዲያ ” ሆኖብኝ ልቀበለው አልተቻለኝም ፣ አልወደድኩትም ! ምስክርነት ግምገማቸውን ያለወደድኩት “የመገናኛ ብዙሃን ውጤቶች አያጠፉም !” ከሚል እሳቤ ተንደርድሬ ሳይሆን ላጠፉት ጥፋት ቅጣት መቅጫ ወፈር ያለ ህግ ተቀምጦ በህግ መጠየቅ ሲገባ ጅምላ ነቀፋን ማቅረብ ባልተገባቸውን ነበር በሚል ነው ። የመንግስት ሃላፊዎች የሰጡት ገለጻና ማብራሪያም የተጻፈውን ህገ ደንብ ከማብራራት አልፎ ጥፋት እየተካሔደ በሆደ ሰፊ መታለፉንና አሁን ግን መንግስት ማምረሩን የሚያስረዳ ከመሆን ያለፈ ፍሬ ነገር የለውም ።
ብቻ ….ገና ከጅምሩ ዘገቢ ፊልሙ ድምጻቸው በሚስብ ጋዜጠኞችና በምስል ቅንብር ደምቆ ፣ መልዕክቱ ግን በህግ በተያዙና በሚፈለጉ ተጠርጣሪ የመገናኛ ባለሙያዎች ላይ ከፍርድ በፊት ጥፋተኝነትን የሚለድፍ ሆኖ ታይቶኛል። ሳጠቃልለው የ “ያልተገሩ ብዕሮች ” ዘጋቢ ፊልም ፍርድ ቤት ገና እያየው ባለውና ባልወሰነባቸው በጦማሪ ጸሃፍት ፣ በአምደኞች እና በነጻው መገናኛ ብዙሃን የሚቀርበውን ክስ ለማጠናከር የተሰራ መሆኑ ያሳብቃል ፣ ወንጀሉን ለማጠናከርም ለውንጀላው ምስክሮች በመንግስት ቴሌቪዥን የሰማሁትን ያህል ተሰማኝ !
ከዘመነ ጃንሆይ ፣ ዘመነ ደርግና ዘመነ ኢህአዴግ የመንግስትን አቋም እያራመዱ በጣም በወረደ ዋጋ ለነዋሪው በየቀኑ እየታተሙ ይቀርባሉ ። ዳሩ ግን ትናንትም ሆነ ሃገር ምድሩን በሚሞላ ቁጥር የመታተማቸውን ያህል ቁም ነገር አላቸው የሚባሉት ገጾች የስራ ፈላጊዎችን ቀልብ የሚስቡት ማስታወቂያዎችና የጨረታ ማስታወቂያዎች ብቻ መሆናቸውን ቢያንስ በደርግና በኢህአዴግ ዘመን አውቃለሁ ። ብዙሃኑን ነዋሪ እውነትንና ጠቃሚ መረጃን ቢይዙ አንኳ አጓጉተውት አይገዛቸውም !

ወደ ኤሌክትሮኒክስ መገናኛ መስኩም ስናመራ የምናየው እውነታ ተመሳሳይ ነው ። ዘመኑ የመረጃ ነው ፣ ዘመነኛ የመገናኛ ተንቀሳቃሽ ስልኮችን ያንጠለጠለው የታደለው ቀርቶ በስማ በለው ከሚነገሩት መስማት የሚናፍቀው የሃገሬ ሰው ቁጥር የትየለሌ ነው። ጭብጥን መረጃ ከሃላፊት ጋር ይዘው ፈርጀ ብዙ በሆነ መንገድ የሚሰራጩ መረጃዎችን በፍቅር የሚከታተለው ወገን መረጃ እንደ እለታዊ ፍጆታው የቆጠረው ይመስላል። ዛሬ ዛሬ ከስልጡን ለውጥ ፈላጊ እስከ መደዴው የኔ ቢጤ ያለ መረጃ መተንፈስ አይቻለውም።
አትኩሮት ሰጥቶ ከሚከታተለው የራዲዮ ፣ ቲቪ መርጦ ጀሮውን ይሰጣል። ለህትመት ውጤት ለሆኑት ጋዜጣና መጽሄቶችን ያለው እየተጋፋ ገዝቶ ፣ የሌላው እየተከራየ መረጃን ይመገባል። ያሻውን ይመርጣል ፣ ያሻውን አንቅሮ የመትፋት ያህል አይቀርባቸውም !
በ ” ባልተገሩ ብዕሮች ” የቀረቡት ባለሙያዎች ያልመረምሩት እውነታ ይህ ነው ። በጥናታዊው ዘገባ የቀረቡት ባለሙያዎች በዋናነት የህዝቡን ነጻ መረጃ የማግኘት መብት አክብረው ሙያዊ ” የተገራ ያልተገራ ብዕር ” ግምገማ አድገው አላሳዩንም ።
ይልቁንም ቀርበው የደሰኮሩበት የህዝብን ገንዘብ መሰረት አድርጎ ከሚንቀሳቀው ኢቲቪ ይልቅ እየፈራ እየተባም ቢሆን ከጽፈኛ ተቃዋሚዎች ልሳንነት የሚደበውን ኢሳትን ይከታተላል ፣ በመንግስት ደጋፊነት የሚፈረጀውን ኢቢኤስን ደረቱን ገልብጦ ማየት ይፈልጋል። የኢትዮጵያ ራዲዮን ትቶ ጀርመን እና አሜሪካን ብሎም በሃገር ቤት የመንግስት እጅ የለባቸውም የሞላቸውን የተመረጡ የኤፍ ኤም አዳዲስ ልዩ ልዩ ፕሮግራሞች ያምናል ፣ ማየትና መስማትን ይመርጣል። የዚህ ሁሉ የነዋሪው ግልጽ ሽሽት ምን ይሆን የሚለው ዳሰሳ መላ ምት ውጤት በዘገባ በቀረቡት ባለሙያዎች ቢነገረን ያምር ነበር ። ” ነበር ባይሰበር ” …

ይህ የሆነው ለምን ይሆን ? ብዙሃን ነዋሪ ምርጫ እንዲህ የሆነው ምን ቢሆን ነው ? እውን ውስጣቸው ባልተገራ ብዕር የታጨቁ መረጃዎች ስለተሞላ ነው ማለት ይቻል ይሆን ? አይመስለኝም በሚል የሚሸፈን ሳይሆን ህዝቡ የፈለገውን ማየት መስማት አይሻምና ነው ባይ ነኝ !…”ያልተገሩ ብዕሮች” ምንጭ እያስተዋለ መርጧልና ያለተገራው ብዕር በሰፊው ያለበትን ቦታ አሳምሮ ተረድቶታል … ! እናም የማይፈልገውን አይቀርበውም ኩሩው ህዝብ እንዲህ ነው !
አይ ” ያልተገሩ ብዕሮች !” ? ጊዜ ደጉ ፣ መስናት ፣ ማየት ፣ መናገር መልካም !
ሰላም ለሁላችሁ !
ነቢዩ ሲራክ

የቴዲ አፍሮ በሰባ ደረጃ ነጠላ ዜማና የበእውቀቱ ስዩም ዕይታ

$
0
0

ሣልሳዊ ቴዎድሮስ ወይም ‹‹ቴዲ አፍሮ ›› በሰባ ደረጃ የተባለ(ች) ነጠላ ዘፈን ለቆልናል፡፡

‹‹በሰባ ደረጃ››ን እኔ ስሰማው እልም ያለ የፍቅር ዘፈን ነው፡፡ፍቅርን ልዩ በሆነ ቦታና ልዩ በሆነ ሥፍራ የሚያሳይ ዘፈን፡፡ በአማርኛ ዘፈን ባህል ውስጥ ቦታን ማስጎብኘት የተለመደ ነው፡፡ ‹‹የሐረር ልጅ ነች ወጣቷ/ጀጎል ነው ቤቷ››አይነት ዘፈን ሞልቶናል፡፡ አብዛኛው ያገራችን ዘፋኝ፣ ያስጎብኝነት ሚናም ደርቦ ሲጫወት ኖሯል፡፡ በዚህ ምክንያት ተፈቃሪዋ ሴት ሁሌም ከታሪካዊ ቦታ አጠገብ ለመወለድ ትገደዳለች፡፡
ቴዲ በዚህ ዜማው ባልተሄደበት መንገድ ሄዷል፡፡ ሲጀምር፣እዚህ ግባ የማይባል ፣ለዓይን የማይሞላ ቦታ መረጠ፡፡ብዙ ጊዜ፣ታሪካዊ ቦታ ሲባል፣አክሱም ላሊበላ፣ፋሲል ሶፍኡመር ጀጎል እንላለን፡፡ ካሜራው በኒህ ቅርሶች ላይ አፍጥጦ ኖሯል፡፡ ታሪክ አክሱም ላይ ጀምሮ ጀጎል ላይ የተጠናቀቀ ይመስል፡፡

ብዙዎቻችን በሸገር ላይ አድልኦ ስንፈጽም ኖረናል፡፡ አዲስ አበባ ለአቅመ ቅርስ የምትበቃ ከተማ አትመስለንም፡፡ሸገር ታሪክ ሲሠራባትና ሲሠራላት እንደኖረች አናውቅም፡፡ ወይም ለማወቅ አንፈልግም፡፡ ቴዲ ይህንን እይታ ቀየረው፡፡

ሁለተኛ፣

ከላይ የጠቀስኳቸው ቅርሶች የጌቶች መታሰቢያ ናቸው፡፡ የምድራዊና ሰማያዊ መሪዎችን የሚወክሉ ናቸው፡፡የስም የለሹን፣የተርታውን ሰው ኑሮ የሚያሳዩ ቅርሶች ግን ደምቀው አልወጡም፡፡አይተን እንዳላየን፣ቸል ብለናቸው ቆይተናል፡፡ቴዲ ግን ማንም ሲወጣበትና ሲወርደበት ለኖረው አንድ መንገድ ዘፈነለት፡፡መዝፈን ቢሉህ ዝም ብሎ መዝፈን ብቻ አይደለም፤ አንድ ውብ የሆነ የፍቅር ታሪክ ተረከበት፡፡ነጠላ ዜማው ከተለቀቀበት ጊዜ አንስቶ ሰባ ደረጃን በድሮ ዓይናችን አናየውም፡፡አሪፍ ጥበብ ዓይን ገላጭ ነው የሚባለው ለዚህ ነው፡፡

የቴዲ አፍሮ በሰባ ደረጃ ነጠላ ዜማና የበእውቀቱ ስዩም ዕይታሦስተኛው ነጥብ፣

ዘፋኞች ልዩ ቦታን ሲያሳዩ ኖረዋል፡፡ቴዲ ደግሞ አንድን ልዩ ዘመን ለማሳየት ሞክሯል፡፡የቴዲን ዘፈን ስሰማ፣ በካሳሁን ግርማሞ ዘመን የኖረ አንድ ሮሚዎ ይታየኛል፡፡ሸዋ ዳቦ ሳይቋቋም፣ከአርመን ሱቅ ፉርኖ በሚሸመትበት ዘመን፣ምኒባስ ሳይገባ ፣ሰዎች ሴቼንቶ የሚሳፈሩበት ዘመን፣ከጄኔራሎች በላይ ሴቼንቶ ነጂዎች ስመጥር የነበሩበት ዘመን፣ሴቶች የጥላቸውን ቁመት አይተው ሰአት ከመገመት ወጥተው፣ክንዳቸው ላይ ሰአት ማሰር የጀመሩበት ዘመን – በዚያ ዘመን የኖረ አፍቃሪ ይታየኛል፡፡አንድን ልዩ ዘመን በሲኒማና በልቦለድ ማሳየት የተለመድ ነው፡፡ በጣም አጭር ቆይታ ባለው ዘፈን ውስጥ ዘመንን ለማሳየት በመሞከር ግን ቴዲ ፋና -ወጊ ይመስለኛል፡፡

ዜመኛ ስላልሆንሁ ስለቴዲ ዜማ ምንም ማለት አልችልም፡፡ያም ሆኖ ፣ግጥሙ የተዋጣለት እንደሆነ መመስከር እችላለሁ፡፡አንድ ቦታ ላይ‹‹አንደ አርሚዴ ሜሪ››የሚል ሐረግ ሰምቻለሁ፡፡ ዜመኛው፣ሜሪ አርምዴን ፣አርምዴ መሪ ብሎ መጥራት የገጣሚነት ነጻነቱ ይፈቅድለታል፡፡ገጣሚ እንደ ህጻን ልጅ፣እንደ እብድና እንደ ቅዱሳን ከቋንቋ ሕግ በላይ ነው፡፡እንደ ጋዜጠኛ፣በሰዋስው ህግ አይታሠርም፡፡እንዲያውም ሳይራቀቁ መግጠም ፣ፈሳሽ ውስጥ ሳይገቡ መስጠም አይታሰብም፡፡

በነገራችን ላይ በድሮ ዘመን በኢትዮጵያ የአባት ስም ከልጅ ስም ቀድሞ ይጻፍ ነበር፡፡ቴዲን ትውፊትም ያግዘዋል ለማለት ፈልጌ ነው፡፡በዚህ ጉዳይ ላይ፣በሚቀጥለው ጽሁፌ እናወጋለን፣

እስከዛ ድረስ ያንን ክራር ወዲህ በል! ታንታራራም ታራራም ታራራም!


የሚካኤል በላይነህ እና የብዟየሁ ደምሴ ድንቅ የሚኒሶታ ሙዚቃ ኮንሰርት (ቪድዮዎች)

$
0
0

ኦገስት 23 ቀን 2014 ዓ.ም ለመጀመሪያ ጊዜ ሚካኤል በላይነህ እና ብዟየሁ ደምሴ ወደ ሚኒሶታ በመምጣት የተሳካ የሙዚቃ ኮንሰርት አቅርበዋል። በርካታ ሕዝብ በታደመበት በዚህ የሙዚቃ ኮንሰርት ላይ ሁለቱም ድምጻውያን ድንቅ የተባለ ሥራዎቻቸውን ከማቅረባቸውም በላይ ድምጻቸው ልክ ሲዲን እንደማድመጥ መሆኑ ታዳሚውን አስገርሟል። ከሙዚቃው ኮንሰርት በሌላ ቦታ የምትገኙ እንድትካፈሉ ዘ-ሐበሻ 4 ዘፈኖችን እንዲህ ታካፍላችኋለች። መልካም መዝናኛ።





የሚካኤል በላይነህ እና የብዟየሁ ደምሴ የሚኒሶታ ሙዚቃ ኮንሰርት (ቪድዮዎች)

Health: በሴቶች ላይ በብዛት የሚከሰተው የኩላሊት ኢንፌክሽን

$
0
0

በሊሊ ሞገስ

በሀገራችን እንደ ቀላል በሽ የሚታዩ፣ ሆኖም ቀስ በቀስ ለተወሳሰበ የጤና ችግር አልፎ ተርፎም ለሞት የሚደርጉ ብዙ በሽታዎች ያሉ ሲሆን፣ የኩላሊት ኢንፌክሽን ከእነዚህ ትኩረት ከማይሰጣቸው አደገኛ በሽታዎች ውስጥ ይመደባል፡፡ የኩላሊት ኢንፌክሽን ኩላሊታችንን ከጥቅም ውጪ ሊያደርገው የሚችል ስለሆነ ማንኛውም ታማሚ ከፍተኛ የሆነ ክትትል በማድረግ ለበሽታው መፍትሄ ማግኘት ይገባዋል፡፡ ከፍተኛ ህክምና ያልተሰጠው ወይም ክትትል ያልተደረገበት የኩላሊት ኢንፌክሽን ለከፍተኛ ስቃይ የሚዳርግ ኢንፌክሽን ከማስከተሉ በተጨማሪ በደም ቧንቧችን በመሰራጨት ለአደገኛ ጉዳት ይዳርጋል፡፡
የኩላሊት ኢንፌክሽን ማለት በሽንት ቧንቧ ላይ በሚደርስ ችግር የሚከሰት ህመም ሲሆን፣ ይህ በኩላሊት አካባቢ የሚገኘው የሽንት መሽኛ ቧንቧ ጉዳት በሚደርስበት ወቅት ህመሙ ይከሰታል፡፡ የሽንት ቧንቧ ከፊኛ እስከ ኩላሊት ድረስ ተዘርግቶ የሚገኝ ሲሆን ባክቴሪ ወደ ቧንቧው አልፎ በሚገባበት ወቅት ሰዎች ለኩላሊት ኢንፌክሽን ይጋለጣሉ፡፡ ኩላሊት ኢንፌክሽን የሚያመጣው ባክቴሪያ ወደ ሽንት ቧንቧ ከገባ በኋላ ለጥቂት ጊዜ ራሳቸውን በማራባት በሽታው በቶሎ እንዲባባስ ያደርገዋል፡፡ የበሽታው ባክቴሪያ ከተለያዩ የሰውነት ክፍሎች የሚመጡ ሲሆን፣ ይህም የሰውነት ክፍል በባክቴሪያ ምክንያት በኢንፌክሽን የተጠቃ ይሆናል፡፡ ባክቴሪያው ወደ ፊኛችን ከመሰራጨት አልፎ ወደ ኩላሊታችን በመዝለቅ የኩላሊት ኢንፌክሽን ያስከትላል፡፡ ከዚህ ውጪም በአርቴፊሻል የሰውነት አካል ምክንያት እንዲሁ አልፎ አልፎ በቀዶ ጥገና ወቅት በሽታው ሲከሰት ይስተዋላል፡፡
kedney infaction and women
የኩላሊት ኢንፌክሽን በተለያዩ ምክንያቶች ሊባባስ ወይም ሊቀሰቀስ ይችላል፤ ከእነዚህም ውስጥ የሴቶች የሰውት ቅርፅ አቀማመጥ፣ የኩላሊት ጠጠር፣ የሽንት ቧንቧ መዘጋት የመሳሰሉት በዋነኝነት ይጠቀሳሉ፡፡ ጾታ በኩላሊት ኢንፌክሽን ህመም ላይ የራሱ የሆነ ተፅዕኖ አለው፡፡ በዚሁ ምክንያት ሴቶች ከወንዶች የበለጠ በኩላሊት ኢንፌክሽን ህመም የመጠቃት ወይም የመያዝ እድላቸው ከፍተኛ ነው፡፡ ይህም የሚሆንበት ዋናው ምክንያት ደግሞ የሴቶች ሽንት ቱቦ ከወንዶች ጋር ሲነፃፀር በጣም አጭር በመሆኑ ነው፡፡ ይህ አጭር ቁመት ባለው የሽንት ቧንቧ ወደ ፊኛ ለመድረስ ጥቂት ጊዜ ብቻ እንዲጓዝ ያደርገዋል፡፡

በሴቶች የሽንት ቧንቧ በብርቶችና በመቀመጫ መካከል ከፍተኛ ቅርበት በመኖሩ ባክቴሪያ ወደ ፊኛ በቶሎ እንዲገባ ያደርጋል፡፡ በዚህም ምክንያት በሽታው ከወንዱ ይልቅ ሴቶች ላይ ያለው ተጋላጭነት ያመዝናል፡፡ ሌላው ለኩላሊት ኢንፌክሽን የሚያጋልጥ ነገር የሽንት ቧንቧ መዘጋት ነው፡፡ ማንኛውም ነገር የሽንት ቧንቧን ሊዘጋ እንደሚችል ጥናቶች ይጠቁማሉ፡፡ ይህ ቱቦ በሚዘጋበት ወቅት የሽንት ጉዞን ይገታል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ ሽንትን ሙሉ በሙሉ ከፊኛ እንዳይወጣ ያግዳል፡፡ ይህ ታዲያ ኩላሊታችንን ለኢንፌክሽን ሊያጋልጠው ይችላል፡፡ የሽንት ቧንቧ ቅርፅ ትክክል አለመሆን የመሳሰሉት ችግሮችም የኩላሊት ኢንፌክሽንን ሲያፋጥኑ፣ የተዳከመ የበሽታ መከላከያ ህዋስ መኖር ኩላሊትን ለኢንፌክሽን ያጋልጠዋል፡፡ እንደሚታወቁት አንዳንድ ህመሞች የበሽታ መከላከያ ህዋስን ያዳክማሉ፡፡ ለምሳሌ ካንሰር፣ ስኳር፣ ኤች.አይ.ቪ ዋነኞቹ የበሽ መከላከያ ህዋስን በማዳከም የሚታወቁ ናቸው፡፡ በእነዚህ ችግሮች ምክንያትም የኩላሊት ኢንፌክሽን ሊባባስ ይችላል፡፡

የኩላሊት ኢንፌክሽን እንደማንኛውም በሽታ የራሱ የሆነ የታወቁ ምልክቶች ያሉት ሲሆን በዋነኝነት ትኩሳት፣ የጎን ህመም፣ የሆድ ህመም፣ በተደጋጋሚ ሽነት መሽናት፣ ሽንት በሚሸናበት ወቅት ቃጠሎ፣ እንዲሁም ከሽንት ጋር የሚወጣ ደም ይጠቀሳሉ፡፡ የኢንፌክሽኑ ምልክት ከዕድሜ እና ከፆታ አኳያ የሚለያ ሲሆን በዕድሜ ሲታይ በታዳጊ ህፃናት ላይ በሽታው ሲከሰት በዋነኝነት ምልክቶቹ የሚሆኑት ተቅማጥ፣ የምግብ ፍላጎት መቀነስ፣ ማቅለሽለሽ፣ ማስመለስ፣ ራስ ምታት የመሳሰሉት ናቸው፡፡ በወጣቶች ደግሞ የበሽታው ዋና ምልክት የሆድ ህመም፣ ከደም ጋር የተቀላቀለ ሽንት፣ ሽንት ቢመጣም ለመሽናት አለመቻል በዋነኝነት ሊጠቀሱ ይችላሉ፡፡ እነዚህ የተጠቀሱትን ምልክቶች በማስተዋል ወደ ሐኪም መሄድ መልካም አማራጭ ነው፡፡ በሽታውን ከታከሙ በኋላም ዳግም ምልክቱ ከታየም ወደ ሆስፒታል በመሄድ የበለጠ ሕክምና መውሰድ አስፈላጊ ነው፡፡ ምክንያቱ ደግሞ የኩላሊት ኢንፌክሽን ከፍተኛ ደረጃ ከደረሰ ወደ ተወሳሰበ የጤና ችግር ሊያደርስ ስለሚችል ነው፡፡
kidney infection causes
ሰዎች በሚታመሙበት ወቅት የሰው ሰራሽ ሽንት መሽኛ ሲገጠምላቸው እንመለከታለን፡፡ ይህ ሰው ሰራሽ መሽኛ ምንም እንኳን ጠቃሚ ቢሆንም ለብዙ ጊዜ በተከታታይ በሽተኛው ከተጠቀመ ግን ሌላ የጤና ችግር ይዞ ሊመጣ ይችላል፡፡ ቱቦው በሰዎች ላይ ለብዙ ጊዜ የሚቆይ ከሆነ ለባክቴሪያ ተጋላጭ ከመሆኑም በላይ፣ ባክቴሪው ደግሞ ለኩላሊት ኢንፌክሽን ሊያጋልጥ ይችላል፡፡ ሽንት ከፊኛ ተነስቶ ወደ ሌላ አቅጣጫ መጓዝ ሌላው የኩላሊትን ኢንፌክሽን የሚያመጣ ምክንያት ነው፡፡ ጥቂት መጠን ያለው ሽንት ከፊኛ ወጥቶ መልሶ ወደ ኩላሊት ወይም ወደ ቱቦ መመለስ ለበሽታው አጋላጭ ይሆናል፡፡ ኩላሊት በሰውነታችን ውስጥ ያለውን ቆሻሻ ደም በማጣራት ወደ ሰርኩሌሽን እንዲመለስ ያደርጋል፡፡ በዚህ ወቅት አንድ ሰው በኩላሊት ኢንፌክሽን የተጋለጠ ከሆነ ኩላሊት ውስጥ ለመጣራት የሚመጣው ደም በባክቴሪያ እንዲበከል ያደርገዋል፡፡ ይህም በሰውነታችን የሚሰራጨው ደም ላይ ችግር ይፈጥራል፡፡ ከዚህ በተጨማሪም በወቅቱ ህክምና ያላገኘ የኩላሊት ኢንፌክሽን ሴቶች ልጅ በሚወልዱበት ወቅት እንዲቸገሩ ያደርጋል፡፡ የሚወለደው ልጅ ኪሎው ትንሽና ጤነኛ እንዳይሆን ሊያደርግም ይችላል፡፡

ማንም ሰው የተለያዩ ደረጃዎችን የጠበቁ ህክምናዎችን በመውሰድ ራሱን ከኩላሊት ኢንፌክሽን መጠበቅ እንደሚችል ጥናቶች ያስረዳሉ፡፡ በእርግጥ ኩላሊት የራሱ የሆነ ምርመራ በላብራቶሪ የሚደረግለት ቢሆንም ያልተጠናከረ ወይም ያልተወሳሰበ የኩላሊት ኢንፌክሽን በምልክቶቹ ብቻ መታወቅ የሚቻል ሲሆን፣ እነዚህን ምልክቶች በመንተራስ ህክምና ማግኘት ይችላል፡፡ በምልክት ብቻ ለታወቀ የኩላሊት ኢንፌክሽን ህመም የተለያዩ አንቲባዮቲክ መድሃኒቶች የሚታዘዙ ሲሆን፤ መድሃኒቶቹም ለአጭር ጊዜ የሚወሰዱና በአፋጣኝ የሚያድኑ ናቸው፡፡ ህመሙ ሳይጠናከር ወደ ሆስፒታል መምጣት ከቻሉ ሰዎች መካከል ከ50 ፐርሰንት በላይ በጥቂት ቀን ውስጥ ያለ ተጨማሪ ህክምና ለመዳን ችለዋ፡፡ ያልጠነከረ ወይም ያልተዋሰበን ኢንፌክሽን ትራይሞቶፍሪም እና ሲልፋሜታክሳዝል የተባሉትን መድሃኒቶች በመውሰድ ብቻ መፈወስ ይቻላል፡፡

ጥናቶች እንደሚጠቁሙት ከሆነ ጡት ማጥባት በከፍተኛ ሁኔታ ህፃናቶች ለኢንፌክሽን እንዳይጋለጡ ማድረግ ሲችል፣ ሌሎችም በርከት ያሉ ቅድመ የመከላከያ መንገዶች ከጤና ባለሙያዎች ይሰጣሉ፡፡ በእርግጥ የመከላከያ መንገዶቹ መቶ በመቶ በሽታውን የሚያመጣው ባክቴሪያ እንዳይከሰት የማድረግ አቅም ባይኖራቸውም እንዳይጠናከር ግን አስተዋፅኦ ያደርጋሉ፡፡ ለአብነት በሽተኞች በየቀኑ የሚወስዱትን ፈሳሽ በከፍተኛ ሁኔታ መጨመር ይገባቸዋል፡፡ ውሃን በከፍተኛ መጠን በየቀኑ መጠታት ኢንፌክሽኑን ይከላከላል፡፡ በከፍተኛ ሁኔታ ፈሳሽ መውሰድ ሽንት ቶሎ ቶሎ እንዲመጣ ሲያደርግ ከሽንት ጋርም ባክቴሪያዎች አብረው በቆሻሻ መልክ እንዲወገዱ ያደርጋል፡፡ ውሃ በብዛት መጠጣት ሽንትን እንደፈለጉ እንዲቋጥሩ አያስችልም፡፡ ሽንት መቋጠር ባክቴሪያ እንዲከማች የሚያደርግ ሲሆን፣ ብዙ ውሃ የሚጠጣ ከሆነ ግን ይህን ማድረግ አያስችልም፡፡ ስለዚህም በቱቦ የሚከማቹት ባክቴሪያዎች እንዲወጡ ይገደዳሉ፡፡ አንዳንድ ባለሙያዎች ጁስ መጠጣት በጣም ጠቃሚ መሆኑን የሚናገሩ ሲሆን፤ ይህ የሆነው ግን መድሃኒት በሚዋጥበት ወቅት መሆን እንደማይገባው ያስረዳሉ፡፡

የግል ንፅህናን መጠበቅ ወይም በፊት ከነበረው የንፅህና አጠባበቅ የተሻለ የንፅህና አጠባበቅ መከተል ሌላው ህመሙን የመከላከያ መንገድ ነው፡፡ ሽንት ከተሸና በኋላ መታጠብ ተገቢ መሆኑን ባለሙያዎች ይናገራሉ፡፡ የብልትን አካል ማጠብ ባክቴሪያ በብልት ወይም በሴት ማህፀን በኩል ወደ ኩላሊት እንዳይገባ ይከላከላል፡፡ የሽንት ቧንቧ ኢንፌክሽን ፆታዊ ግንኙነትን ተከትሎ የመከሰት ዕድሉም የሰፋ ነው፡፡ ምክንያቱም ከግንኙነት በኋላ ባክቴሪያው ወደ ቱቦው በቀላሉ ሊገባ ስለሚችል ነው፡፡ ስለዚህም ከግንኙነት በኋላ በአስቸኳይ ሽንት መሽናት ተገቢ ሲሆን ይህን ማድረግ ባክቴሪያው ከሽንት ጋር አብሮ እንዲወጣ ያደርጋል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ ከግንኙነት በፊት ብልትን ማፅዳት የማስፈለጉን ያህል ሽቶና ዲዮደራንት የመሳሰሉትን ኬሚካል ያላቸውን ቅባቶች በብልት አካባቢ ፈፅሞ መጠቀም አያስፈልግም፡፡

የኩላሊት ኢንፌክሽን በተለያየ ደረጃ ህክምናው የሚሰጥ ሲሆን፣ ከቀላል ህክምና እስከ አልጋ ማስያዝ ያደርሳል፡፡ ቀላሉ ያልተወሳሰበ የኩላሊት ኢንፌክሽን ችግር በአንቲባዮቲክ እንደሚድን ሁሉ የተወሳሰበና ቶሎ ህክምና ያላገኘ ህመም ሆስፒታል እስከማስተኛት ለከፋ ችግር ያደርሳል፡፡ አደገኛ ደረጃ የደረሰ የኩላሊት ኢንፌክሽን ህመም በማንኛውም ሐኪም ሳይሆን ከፍተኛ ክትትል ስለሚያስፈልገው በስፔሻሊስቶች መታየት ይገባል፡፡ በይበልጥ ዳግም እንደገና ለተነሳ (ላገረሸ) የኩላሊት ኢንፌክሽን ህመም ከፍተኛ ክትትል ስለሚያስፈልግ ወደ ስፔሻሊስት በመሄድ ማማከር ጠቃሚ መሆኑን የህክምና ባለሙያዎች ያስረዳሉ፡፡ የከፋ ኩላሊት ኢንፌክሽን እስከ ኦፕራሲዮን ሊያደርስም ይችላል፡፡

የኩላሊት ኢንፌክሽን ከወንዶች ይልቅ ሴቶች ላይ በብዛት የሚከሰት ሲሆን በርካታ ሴቶች ቢያንስ ቀላል የኩላሊት ኢንፌክሽን በወጣትነት ጊዜያቸው ሊያጋጥማቸው እንደሚችል ጥናቶች ይጠቁማሉ፡፡ ወንዶች ከሴቶች ጋር ሲነፃፀሩ በኢንፌክሽን የመያዝ ዕድላቸው ከፍተኛ ከመሆኑ በተጨማሪ ወጣት ወንዶች ከ50 ዓመት በላይ ካሉ ወንዶች ጋር ሲነፃፀር የመያዝ ዕድላቸው ዝቅተኛ ነው፡፡ በወንዶች ላይ በኢንፌክሽኑ የመያዝ ዕድሉ ሲሰፋ የሚስተዋለው ዕድሜያቸው ከ50 ዓመት በላይ ባሉት ላይ ነው፡፡ በሰለጠኑ ሀገራት ህመሙ በወጣት ተማሪዎች ላይ እየጨመረ ሲገኝ፣ ሴቶች ተማሪዎች ከወንድ ተማሪዎች የበለጠ እየተጠቁ ይገኛሉ፡፡ በትምህርት ቆይታቸው ወቅት ቢያንስ ከአምስት ሴቶች አንዷ በኩላሊት ኢንፌክሽን እንደምትጠቃም ተገልጿል፡፡

Zehabesha.com

በትግራዮች እና በአፋሮች መካከል በተነሳ የድንበር ይገባኛል ግጭት የአንድ ሰው ሕይወት ማለፉ ተዘገበ

$
0
0

(ዘ-ሐበሻ) አሁን ለዘ-ሐበሻ የደረሰው መረጃ እንደሚያመለክተው በአፋር ክልል በሰሜን ዞን በኮናባ ወረዳ ነዋሪዎች እና በትግራይ ክልል የአፅቢ ወንባርታ ወረዳ ነዋሪዎች መካከል ግጭት የተቀሰቀሰ ሲሆን እስካሁን የአንድ ሰው ሕይወት ማለፉ ተዘግቧል።

(የሕወሓት መንግስት ኢትዮጵያን የሚያስ ተዳድርበት ካርታ)

(የሕወሓት መንግስት ኢትዮጵያን የሚያስ ተዳድርበት ካርታ)


አኩ ኢቢን ከአፋር ለዘ-ሐበሻ ባደረሰው መረጃ በኮናባ ወረዳ የዋህደስ ቀበለ አፋሮችና በአፅቢ ወረዳ ኦሳት ቁሼት ከ1 አመት በፊት የድምበር ይገባኛል ያለመገግባባት የነበረ መሆኑ በተደጋጋሚ የተዘገበ ሲሆን ዛሬ ከሳዓት በኋላ በኢትዮጵያ ሰዓት አቆጣጠር 8:30 ጀምሮ ይህ ዜና እስከተጠናከረበት ጊዜ ድረስ ግጭት ላይ ይገኛሉ።

በድንበር ይገባኛል ግጭት የተነሳ በተለያዩ የኢትዮጵያ ከተሞች ከዚህ ቀደም ንጹሃን ዜጎች ሕይወት ማለፉ የሚታወስ ሲሆን አሁንም በአፋሮች እና በትግራዮች መካከል የተነሳው ግጭት ሥርዓቱ የፈጠረው የዘረኝነት አስተዳደር ውጤት ነው የሚሉ አስተያየት ሰጪዎች አሉ።

ለዘ-ሐበሻ መረጃውን ያደረሰው አኩ ኢቢን ኮናባ መተው እየተዋጉ ያሉት የወታደር ልብስ የለበሱ የሚሊሻ አባላት ናቸው ሲል እስካሁን በዚህ ግጭት 1 ሰው ሲሞት 2 ሰዎች ደግሞ ቆስለዋል ብሏል። በሞተው ሰው ጉዳይ ዘ-ሐበሻ ከመንግስት ወገኖች ለማጣራት ያደረገችው ጥረት ባይሳካም የድንበር ግጭቱን ለማብረድ ከመንግስት በኩል እየተደረገ ያለው ዝግመተኛ ሥራ የአካባቢውን ነዋሪዎች እንዳስቆጣ ምንጮች ገልጸውልናል።

በዚህ ግጭት ዙሪያ ተጨማሪ መረጃዎች እንደደረሱን እንመለሳለን።

‹‹የፀረ ሽብር ህጉ ሰለባዎች ››በፍኖተ ነፃነት ዝግጅት ክፍል የተዘጋጀ ዶክመንታሪ

$
0
0

‹‹የፀረ ሽብር ህጉ ሰለባዎች ››በፍኖተ ነፃነት ዝግጅት ክፍል የተዘጋጀ ዶክመንታሪ


‹‹የፀረ ሽብር ህጉ ሰለባዎች ››በፍኖተ ነፃነት ዝግጅት ክፍል የተዘጋጀ ዶክመንታሪ

አስር ኤርትራውያን ወደ ኢትዮጵያ ሊገቡ ሲሉ መገደላቸውን ሱዳን ትሪቢዩን ዘገበ

$
0
0

ከመስከረም አያሌው

የኤርትራ ድንበር ጠባቂዎች ወደ ኢትዮጵያ ሊገቡ የነበሩ አስር ኤርትራውያንን መግደላቸው ተገለፀ።

eritrea_ethiopia_border+mapሱዳን ትሪቡን ከግድያው የተረፈን አንድ ሰው ጠቅሶ እንደዘገበው፣ ወደ ኢትዮጵያ ሊገቡ ከነበሩ 18 ኤርትራውያን መካከል አስሩ በኤርትራ ድንቡ ጠባቂዎች መገደላቸው ተገልጿል። ከሟቾቹ መካከልም የ18 ወራት ወታደራዊ ግዴታዋን የተወጣች ሴት እንደምትገኝበት ታውቋል። ሳሙኤል ጌዲዮን የተባለው ከግድያው ያመለጠው ግለሰብ እንደገለፀው ወደ ኢትዮጵያ ለመግባት መንገድ ከጀመሩት 18 ኤርትራውያን መካከል አስሩ በድንበር ጣባቂዎች የተገደሉ ሲሆን፣ እርሱን ጨምሮ ሶስቱ ወደ ኢትዮጵያ ገብተዋል። ሳሙኤል እንደገለፀው ከሆነ የቀሪዎቹ አምስቱ ኤርትራውያን እጣ ፈንታ ምን እንደሆነ አልታወቀም። እንደ ሳሙኤል ገለፃ የድንበር ጠባቂዎቹ በተጓዦች ላይ ያለ ምንም ቅድመ ማስጠንቀቂያ ተኩስ የከፈቱባቸው ሲሆን በ18 ወራት ወታደራዊ ግዴታዋን ተወጥታ ያጠናቀቀችዋን ወጣት ጨምሮ አስር ኤርትራውያን የተኩሱ ሰለባ ሆነዋል።

ኤርትራ ሀገራቸውን ትተው ወደ ሌላ ሀገር የሚሰደዱ ኤርትራውያንን የመግደል ፖሊሲ እያራመደች መሆኑ የተገለፀ ሲሆን፣ ባለፉት ሁለት ዓመታት ውስጥም በመቶዎች የሚቆጠሩ ወጣት ኤርትራውያን በድንበር ጠባቂዎች እንደሞቱ መረጃዎች ያመለክታሉ። ከኤርትራ ወጥተው የሚሰደዱ ኤርትራውያን ሀገራቸውን እንደከዱ ተደርገው የሚቆጠሩ ሲሆን፤ ከሀገር ሳይወጡ ከተያዙም ብዙዎቹ ለእስር እና ለሰብአዊ መብት ረገጣ የሚደረጉ ሲሆን፣ በተለይ ከተቃዋሚ ኤርትራውያን ጋር ግንኙነት አላቸው ብለው የተገመቱ በርካቶች ደግሞ የሞት ፍርድ ይፈረድባቸዋል።

አሁንም በርካታ ወጣት ኤርትራውያን በሀገሪቱ ያለውን መቋጫ የሌለው ከባድ ወታደራዊ ግዴታ ሰብዓዊ መብት ጥሰት እና የመልካም አስተዳደር እጦት በመሸሽ በዚህ የድንበር ጠባቂዎች አምልጠው ወደ ጎረቤት ሀገራት እየገቡ መሆኑም ተገልጿል።

ምንጭ፡ ሰንደቅ ጋዜጣ (ዛሬ በአዲስ አበባ ታትሞ የወጣ)

Sport: ፑቲንና የሩሲያ እግር ኳስ

$
0
0

በራሺያ እግርኳስ ተፅዕኖ ፈጣሪ ናቸው የሚባሉት የክለብ ባለስልጣናት ለአንድ ጉዳይ ያስፈለገው በቅርቡ ወደ ራሺያ የተቀላቀለችውን የክሬሚያ የእግርኳስ ክለቦች እጣ ፈንታ ለመወሰን ነው፡፡ በባለስልጣናቱ ድምፅ ውስጥ ግን ፍርሃት ይሰማል፡፡ ጭንቀታቸውንም መታዘብ ይቻላል፡፡ ሶስቱን የክሬሚያ ክለቦች ወደ ራሺያ ሊግ መቀላቀል ሊያመጣ የሚችለው አስከፊ ውጤት አሳስቧቸዋል፡፡ የራሺያ ክለቦች ከአውሮፓ ውድድሮች ሊታገዱ እንደሚችሉ በማሰብ ደንግጠዋል፡፡ ሀገራቸው ከ2018 የዓለም ዋንጫ አስተናጋጅነት ልትሰረዝ እንደምትችል በመገመትም ጭንቀት ወጥሮ ይዟቸዋል፡፡ ከሁሉም በላይ ያሰጋቸው ግን ሌላ ጉዳይ ነበር፡፡ ሶስቱን ክለቦች ወደ ራሺያ ሊግ አለመቀላቀል ሊያስቆጣው የሚችል አንድ ሰው አለ – የራሺያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን፡፡
putin
የእነዚህ ሰዎች ስብሰባ ተቀርጿል፡፡ ቅጃ ደግሞ በአንድ የራሺያ ጋዜጣ ላይ ወደ ፅሑፍ ተቀይሮ ወጥቷል፡፡ የራሺያን እግርኳስ የሚቆጣጠሩት ባለስልጣናት ሊግ እንዲወዳደሩ ቢፈቅዱ ከምዕራባውያኑ ሊደርስባቸው የሚችለውን ማዕቀብ በሌላ በኩል ይህን ባያደርጉ ደግሞ ከፑቲን የሚደርስባቸው አፀፋ ወጥሮ ይዟቸው ለመወሰን ተቸግረዋል፡፡ በቅጂው ላይ ከፑቲን መመሪያን ለመቀበል በመወሰን መፍትሄ ላይ ደርሰዋል፡፡ ይህ ደግሞ የሀገራት እግርኳስ ማህበራት ከማንኛውም ፖለቲካዊ ተፅዕኖ ነፃ መሆን እንዳለባቸው የሚያዘውን የፊፋ ህግ የሚጥስ ነው፡፡ ብዙዎች ተቀርፆ በወጣው ካሴት ላይ ጥርጣሬ ቢኖራቸውም አንድ የስብሰባው ተሳታፊ ለሞስኮ ራዲዮ ውይይቱ እንደተካሄደ ገልፀዋል፡፡

ስብሰባው ከፍተኛ ባለሀብት የሆኑት ተሳታፊዎቹ የራሺያ መንግሥት ምን ያህል እንደሚፈሩ ያሳየ ነበር፡፡ ፑቲን ያላቸው ተፅዕኖ እስከምን ድረስ እንደሆነም ያመለከተ ነው፡፡ የምዕራባውያኑ ሀገራት ማዕቀብ ሀገሪቱ ላይ ያሳረፈውን ተፅዕኖም እስከየት ድረስ እንደደረሰ በስብሰባው ተሳታፊዎች መነፅር መመልከት ይቻላል፡፡ ከውይይቱ ተሳታፊዎች መካከል የሀገሪቱ ትልልቅ ባለሀብቶች ይገኙበታል፡፡ ከእነዚህ መካከል ሱለይማን ኬሪሞቭ አንዱ ናቸው፡፡ የሰውዬው ሀብት በዓለም 72ኛ ደረጃ ላይ አስቀምጧቸዋል፡፡ የሀገሪቱ ትልልቅ ክለቦች ዜኒት ሴንት ፒተርስበርግ እና ሲኤስኬኤ ሞስኮው መሪዎች በስብሰባው ተሳትፈዋል፡፡ የራሺያ መንግሥት የምድር ባቡር ኃላፊ እና የፑቲን የቅርብ ጓደኛ የሆኑት ቭላድሚር ያኩኒንንም በውይይቱ ተገኝተዋል፡፡ የእግርኳሱ ባለስልጣናት በክሬሚያ ክለቦች እጣ ፈንታ ላይ ተሰባስበው እንዲወስኑ የታዘዙት በራሺያ እግር ኳስ ማህበር ነው፡፡ የዩክሬን ግዛት የነበራቸው ክሬሚያ ራሺያን የተቀላቀለችው ባለፈው ማርች ነበር፡፡ ባለፈው ሳምንት የራሺያ የስፖርት ሚኒስቴር ሶስቱ የክሬሚያ ክለቦች ሲምፌሮፓል፣ ሴባስቶፖል እና ያልታ የሀገሪቱን የታችኛውን ዲቪዚዮን እንደሚቀላቀሉ አስታውቆ ነበር፡፡ በዚህ የተነሳ የዩክሬን እግርኳስ ፌዴሬሽን ‹‹ክለቦቼን ተሰርቄያለሁ›› ሲል ቅሬታውን አሰምቷል፡፡ ባለፈው ማክሰኞ ግን ሶስቱ ክለቦች በራሺያ ዋንጫ የመክፈቻ ጨዋታቸውን አድርገዋል፡፡

በስብሰባው የተሳተፉ አብዛኞቹ ባልጣናት ማዕቀብ ቢያስከትልም ውሳኔ ላይ መድረስ እንዳለባቸው አውቀውታል፡፡ ባለስልጣናቱ አስቸጋሪ ሁኔታ ውስጥ ነበሩ፡፡ የክሬሚሊንን መንገድ ከተከተሉ ከምዕራባውያኑ ማዕቀብ ይጠብቃቸዋል፡፡ ይህን ካላደረጉ ደግሞ የፑቲንን አይን ለማየት አይደፍሩም፡፡ ሰርጌ ስቴጋሺን የቀድሞ የራሺያ የደህንነት ሚኒስትር እና የሀገሪቱ እግርኳስ ማህበር ስራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባል ናቸው፡፡ በድብቅ በወጣው ካሴት ላይ በስብሰባው ‹‹ችግር ውስጥ ነን›› ማለታቸው ተደምጧል፡፡

የሲኤስኬኦ ሞስኮው ፕሬዝዳንት ኤቭጌኒ ጊነር ድምፅ በመስጠታቸው እነርሱ ባልተሳተፉበት ውሳኔ የመጣ መዘዝ ገፈት ቀማሽ እንደሆኑ በመናገር ቅሬታ አቅርበዋል፡፡ ጊነር ‹‹እኛ ያልተሳተፍንበት ውሳኔ›› ያሉት የክሬሚያን በራሺያ መጠቅለል ነው፡፡ ‹‹ተመለከቱ! እርሱ ምንም የሚያጣው ነገር የለም›› ብለው የእግርኳስ ማህበሩን ፕሬዝዳንት ኒኮላይ ቶልስቲይክ ሲተቹ ተደምጠዋል፡፡ ‹‹እኔ ግን የምመራው ክለብ አለኝ፡፡ (ክለቦቹ እንዲቀላቀሉ በመወሰናችን) የ2018 ዓለም ዋንጫ አስተናጋጅነታችንን ይነጥቁናል፡፡ ለምን? ምክንያቱም በፕሬዝዳንቱ ስም የተሸፈኑ ጥቂት ብልጥ ሰዎች ‹‹እደግፋለሁ›› ወይም ‹‹አልደግፍም›› የሚለው ላይ ምልክት እንድናስቀምጥ በማስገደዳቸው ነው››

አሜሪካ እና የአውሮፓ ህብረት ራሺያ ላይ በተከታታይ ማዕቀብ ጥለዋል፡፡ ሀገሪቱ በምስራቅ ዩክሬን በተከሰተው ቀውስ ላይ ቤንዚን እያርከፈከፈች እንደሆነ ማመናቸው ደግሞ ምክንያታቸው ነው፡፡ በዚያ ላይ አፍቃሪ ራሽያ የሆኑትንና የዩክሬን መንግሥት ጋር ጦርነት የሚያደርጉትን ቡድኖች ትደግፋለችም ይሏታል፡፡ የመጀመሪያው ዙር ማዕቀብ ኢላማ ያደረገው ሉፑቲን ቅርብ የሆኑ ሰዎችን ነው፡፡ የምድር ባቡር ኃላፊ ያኩኒን አንዱ ናቸው፡፡ በስብሰባው የሥራ ጓደኞቻቸውን ‹‹አርበኞች አይደላችሁም›› ሲሉ እንደዘለፏቸው ተሰምቷል፡፡ ከዚያ በኋላ የተጣሉት ማዕቀቦች የራሺያ የፋይናንስ ተቋማትን ኢላማ ያደረጉ ናቸው፡፡ ‹‹ምንም ብታደርጉ ማዕቀቡ አይቀርም›› ብለው ያኩኒን ጓደኞቻቸውን እንዳስፈሯሯቸው የስብሰባውን ቅጂ በፅሑፍ ያተመው ጋዜጣ አስነብቧል፡፡ ‹‹ተንበርክካችሁ ብትለምኗቸው እንኳን ማድረጋቸው አይቀርም፡፡ ይገባችኋል? ስለዚህ ወይ ከሀገሪቱ ውጡ አልያም እንደ ዜጋ አስቡ›› ማለታቸውም ተሰምቷል እንደ ጋዜጣው ዘገባ፡፡

በስብሰባው የእግርኳሱ ባለስልጣናት በክሬሚያ ጉዳይ ላይ ድምፅ የማይሰጡበትን መላ ሲያፈላልጉ ነበር፡፡ የስፖርት ሚኒስትሩ ክለቦችን ወደ ራሺያ ሊግ የመቀላቀል ውሳኔ ከክሬሚሊን ቤተ መንግሥት በቀጥታ የተላለፈ ትዕዛዝ መሆን አለመሆኑንም ተጠያይቀዋል፡፡ የእግርኳሱ መሪዎች ለክሬሚያ ክለቦች ብለው በአውሮፓ መድረክ በመሳተፍ የሚያገኙትን ጥቅም ላለማጣት ቢያንገራግሩም በቢሊዮነሮቹ እንኳን የፑቲን ቃል ምን ያህል ኃይል እንዳለው በስብሰባው ታይቷል፡፡ ሴርጌይ ጋሊትስኪ ቢሊዮኔር እና የራሺያው ክለብ ክራስኖዳር ቺፍ ኤግዜኪዩቭ ናቸው፡፡ ‹‹ከላይ የመጣ (ከፑቲን) ትዕዛዝ ከሆነ ጥያቄ ማንሳት የለብንም›› ሲሉ ተደምጠዋል፡፡ የእግርኳስ ማህበሩ ፕሬዝዳንት ቶልስቶይክ የስፖርት ሚኒስትሩ ቪታሊ ሙትዋ የክሬሚያን ክለቦች ጉዳይ እንደፈቱት ሲናገሩ የስብሰባው አንድ ተሳታፊ ‹‹ሚኒስቴሮቹ ምንም ነገር አያገባቸውም›› ብለዋል፡፡ ዋናው የፑቲን ትዕዛዝ እንደሆነ ለማሳየት የተናገሩት ይመስላል፡፡

የስብሰባው ተሳታፊዎች ሊያደርጉ የማይፈልጉት አንድ ነገር ቢኖር የፑቲንን ቃል አለማክበር ነው፡፡ የዜኒት ሴንት ፒተርስበርግ ክለብ ፕሬዝዳንት የሆኑት አሌክሳንደር ዴይኮቭ ብዙ ገንዘብ የሚያስገኝላቸውን የቻምፒዮንስ ሊግ ቦታ ለማጣት መዘጋጀታቸውን በስብሰባው ተናግረዋል፡፡ የፕሬዝዳንት ፑቲንን ቃል ለማክበር ማለት ነው፡፡ ‹‹ያለ አውሮፓ መኖር እንችላለን፡፡ ስለ ዓለም ዋንጫው የምናወራ ከሆነ ግን ጉዳዩ ፖለቲካዊ ጥያቄ ነው›› ይላሉ ዴይኮቭ፡፡ ባለስልጣናቱ በእጅጉ የተጨነቁት ራሺያ በ2018 ዓለም ዋንጫን ከማስተናገድ የሚያግዳት ውሳኔን ላለማስተላለፍ ነው፡፡ የብሪታኒያ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ኒክ ክሌግ የራሺያን የ2018 ዓለም ዋንጫን አስተናጋጅነትን ማንሳት የማዕቀቡ አካል እንዲሆን እቅድ አቅርበው ነበር፡፡ ቢያንስ ለጊዜው ሰሚ አላገኙም፡፡ ራሺያውያኑ ግን ተጨንቀዋል፡፡
‹‹የዓለም ዋንጫ አስተናጋጅነቱ ለእንግሊዝ ይሰጣል›› ሲሉ የሲኤስኬኤ ፕሬዝዳንት ጊነር በስብሰባው ላይ ተናግረዋል፡፡ ‹‹የዚያን ጊዜ ፑቲን የሚያሳድደው የእግርኳስ ማህበሩ ሊቀመንበር ቶልስቲይክን አይደለም፡፡ እኛ እዚህ የተቀመጥነውን እንጂ›› ብለው ውሳኔያቸው የሚያመጣውን መዘዝ ለጓደኞቻቸው አስረድተዋል፡፡

ይህ በድብቅ የወጣው የስብሰባው ተሳታፊዎች የተቀረፀ ድምፅ ‹‹ነፃ ናቸው›› የሚባሉትን አካላት ሳይቀር የክሬሚሊን መንግሥት እንዴት እንደፈለገ እንደሚያደርጋቸው ያሳያል፡፡ የስብሰባው ተሳታፊ ባለስልጣናት የመንግሥት ከፍተኛ አመራሮች ከእነርሱ ምን እንደሚፈልጉ ስላላወቁ ግራ ገብቷቸው ተስተውለዋል፡፡ ‹‹በአሁኑ ሰዓት ኃይለኛ ፖለቲካዊ ጨዋታ እየተካሄደ ነው›› ይላሉ የክሮስኖዳሩ ቺፍ ኤግዚኪዩቲቭ ጋሊትስኪ፡፡ ‹‹የሀገሪቱ የመጀመሪያ ሰው (ፑቲን) ይህን ነገር ላይፈልገው ይችላል? እርሱን ሳንጠይቅ ውሳኔ ላይ ብንደርስ አያመሰግነንም፡፡ በመጨረሻ ተሰብሳቢዎቹ በውሳኔያቸው ፑቲን ምን ይሉ ይሆን? ብሎ ከመጨነቅ ከበላይ አካል መመሪያ እንዲመጣላቸው ጠይቀዋል፡፡ እፎይ ማለታቸውን ያወቁ ጋሊትስኪ ውሳኔያቸው ምክር መጠየቅ እንደሆነ ተናግረዋል፡፡ ‹‹ፖለቲካዊ ምክር››

ከጅቡቲው ፕሬዚዳንት ግድያ ሙከራ በስተጀርባ ያለው ማን ነው?

$
0
0

ከመላኩ ጸጋው/ሰንደቅ ጋዜጣ

የጅቡቲው ፕሬዝዳንት ኢስማኤል ኦማር ጌሌ በአዲስ አበባ ሰሞኑን የተካሄደውን የኢጋድ ስብሰባ ተካፈለው ሲመለሱ ከተቃጣባቸው የግድያ መትረፋቸውን የሀገሪቱን የውጪ ጉዳይ ሚኒስትር መሀመድ አሊ የሱፍን ጠቅሶ ብሉምበርግ ትናንት ባሰራጨው ዘገባ ገልጿል። በሀገሪቱ ዋና አውሮፕላን ማረፊያ ቅጥር ግቢ ውስጥ ታጣቂ ወታደር በከፈተው ተኩስ የፕሬዝዳንቱ የግል ዶክተር ሁለት ጊዜ ደረታቸው አካባቢ እንዲሁም አንድ ጥይት ደግሞ ጭንቅላታቸውን በጨረፍታ ያገኘው መሆኑ ታውቋል። ተኩስ ከመከፈቱ ከጥቂት ደቂቃዎች በፊት ፕሬዝዳንቱ ከኤርፖርቱ ወደ ቤተመንግስታቸው ያመሩ መሆኑን ዘገባው ያመለክታል።
Djibouti President ismael
ተኩሱን የከፈተው ወታደር በቁጥጥር ስር የዋለ ሲሆን ከዚህ ጥቃት ጀርባ የማን እጅ እንዳለ የማጣራቱ ስራ እየተካሄደ ነው ተብሏል። ባለፈው ግንቦት ወር በአንድ የጅቡቲ ሬስቶራንት ውስጥ የአጥፍቶ መጥፋት ጥቃት መድረሱን ተከትሎ አልሸባብ ኃላፊነቱን ከወሰደ በኋላ ሀገሪቱ የፀጥታ ጥበቃዋን ለማጠናከር ተገዳለች። በዚሁ ጥቃት የበርካታ የውጪ ሀገራት ዜጎች የመቁሰል አደጋ የደረሰባቸው ሲሆን ይህም በሀገሪቱ ታሪክ የመጀመሪያው የአጥፍቶ መጥፋት ጥቃት የተባለለት ነው። ጥቃቱ ከተፈፀመ በኋላ አሜሪካ ወደ ጅቡቲ የሚጓዙ ዜጎቿ ጥንቃቄ እንዲያደርጉ ማስጠንቀቂያ የሰጠች ሲሆን እንግሊዝም አልሸባብ በጅቡቲ በሚገኙ የምዕራባውያን ጥቅሞች ላይ ሌሎች የሽብር ጥቃቶችን ሊሰነዝር የሚችል መሆኑን በወቅቱ ገልፃ ነበር።


ሱዳን ከኢትዮጵያ የምትገዛውን የኤሌክትሪክ ኃይል ለኤርትራ ለመሸጥ መዘጋጀቷ ተሰማ

$
0
0

ኢትዮጵያ በተዘዋዋሪ መሸጡ አያሳስበኝም አለች

የሱዳን መንግሥት ከኢትዮጵያ ለመግዛት ከተስማማው አንድ መቶ ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል ውስጥ መጠኑ ይፋ ያልተደረገ ኃይል ለኤርትራ ለመሸጥ ዝግጅት ላይ መሆኑ ተሰማ፡፡

Kenya-Ethiopia-electricity-300x200የሱዳን የኤሌክትሪክ ኃይል ማሰራጫ ኩባንያን ዋቢ ያደረገው ኢነርጂ ቢዝነስ ሪቪው ድረ ገጽ ባስነበበው ዘገባ መሠረት፣ በምሥራቃዊ ሱዳን በኩል ከከሰላ ግዛት ተነስቶ ወደ ኤርትራ የሚዘረጋ የ45 ኪሎ ሜትር የኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር መዘርጋት ተጀምሯል፡፡

ከሁለት ዓመት በኋላ ይጠናቀቃል ተብሎ የሚጠበቀው የህዳሴው ግድብ የኃይድሮ ኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ሱዳን፣ ደቡብ ሱዳን፣ ጂቡቲ፣ ኬንያ፣ ሶማሊያ፣ ግብፅና አሁን ደግሞ ኤርትራ ተጠቃሚ ይሆኑበታል ተብሎ ስድስት ሺሕ ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል እንዲያመነጭ በመገንባት ላይ ይገኛል፡፡ ባለፈው ዓመት ሱዳንና ኢትዮጵያ የድንበር ተሻጋሪ ኃይል ማሰራጫ መስመርን በጋራ ማስመረቃቸው የሚታወስ ነው፡፡

ሱዳን ወደ ኤርትራ ልትሸጥ ዝግጅት መጀመሯን በማስመልከት ሪፖርተር ያነጋገራቸው የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ፣ የኃይል ሽያጭ ስምምነቱ በኢትዮጵያና በሱዳን መካከል የተደረገ መሆኑን አስታውሰዋል፡፡ ‹‹ይህም ሆኖ ሱዳን ከኢትዮጵያ የገዛችውን የኤሌክትሪክ ኃይል ለማን እንደምታስተላልፍና ከማን ጋር እንደምትነግድ ለመቆጣጠር አንችልም፣ ሉዓላዊነቷም አይፈቅድልንም፤›› ሲሉ አስረድተዋል፡፡

‹‹ሱዳን ከማን ጋር እንደምትነግድ በሉዓላዊነቷ ላይ ማዘዝ አንችልም፤›› ያሉት አምባሳደር ዲና፣ ሱዳን ከኢትዮጵያ የገዛችውን ኤሌክትሪክ ኃይል በተዘዋዋሪ መንገድ ለኤርትራ መሸጧ ላይ ችግር የለውም ብለዋል፡፡ ‹‹የምንፈልገው የአካባቢው አገሮች ሀብቱን ተጠቅመው በሰላም መጎራበታቸውን ነው፤›› ከማለታቸውም ባሻገር፣ የኤሌክትሪክ ኃይል ብቻም ሳይሆን ሌላውም የኢትዮጵያ ምርት ከኤርትራ ባሻገር ለማንኛውም አገር ቢቀርብ፣ ኢትዮጵያ ችግር እንደሌለባት አስታውቀዋል፡፡

በቅርቡ ለኤርትራ ቴሌቪዥን የተናገሩት ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ኢትዮጵያ ከህዳሴው ግድብ ከምታመነጨው የኤሌክትሪክ ኃይል የመግዛት ዕቅድ እንዳላቸው አስታውቀው ነበር፡፡ ፕሬዚዳንቱ የኤርትራ አውሮፕላን ማረፊያን ጨምሮ ትልልቅ የመንግሥት ተቋማት በኃይል አቅርቦት እጥረት ሳቢያ በአግባቡ አገልግሎት መስጠት እንደተሳናቸውና ኃይል ከኢትዮጵያ ለመግዛት መታቀዱን ተናግረዋል፡፡ ፕሬዚዳንት ኢሳያስ ይህንን ከተናገሩ ከጥቂት ጊዜ ቆይታ በኋላ ኤርትራ በሱዳን በኩል ኃይል ለመግዛት መዘጋጀቷ ግን የፕሬዚዳንቱን መግለጫ ግራ የሚያጋባ አድርጎታል፡፡ በሱዳን አማካይነት ኤርትራ የኤሌክትሪክ ኃይል ልትገዛ ነው የሚለው መረጃ መረጋገጥ አለበት በማለት አምባሳር ዲና ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡

ሱዳን ከኢትዮጵያ ለምትገዛው ኃይል በኪሎ ዋት አወር 0.6 ዶላር እንደምትከፍል ይጠበቃል፡፡ በዚህ አነስተኛ መጠን ገዝታ ለኤርትራ በምን ያህል ዋጋ ልትሸጥ እንደምትችልና ምን ያህል ሜዋ ጋት ኃይል እንደምታቀርብላት ለማወቅ አልተቻለም፡፡

Ethiopian Reporter

እየተገባደደ ባለው ክረምት ስድስት ሰዎች በጐርፍ አደጋ ሕይወታቸው አልፏል

$
0
0

ታምሩ ጽጌ

 በብዙ ሚሊዮን ብር የሚገመት ንብረት ወድሟል -መርካቶ ጆንያ ተራ ለሁለተኛ ጊዜ የእሳት አደጋ ደረሰበት

የክረምት ወቅት ከገባ ጀምሮ ሊጠናቀቅ ጥቂት ጊዜ እስከቀረው እስከ ነሐሴ 20 ቀን 2006 ዓ.ም. ድረስ በአዲስ አበባ ከተማ ብቻ ስድስት ሰዎች በጐርፍ አደጋ ሕይወታቸው ማለፉ ታወቀ፡፡

ሕይወታቸው በጐርፍ አደጋ ካለፉት ስድስቱ ሰዎች መካከል ሦስቱ በአራዳ ክፍለ ከተማ ወረዳ አንድ ቴዎድሮስ አደባባይ ኤክስትሪም ሆቴል አካባቢ ሲሆኑ፣ ሦስቱ በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ሃና ማርያም አካባቢ፣ በቦሌ ክፍለ ከተማ ቦሌ ቡልቡላና ሰሚት ኮንዶሚኒየም አለፍ ብሎ በሚገኙት ቦታዎች መሆኑ ታውቋል፡፡

news addisከሌላው የክረምት ወቅት ጋር ሲነፃፀር በዘንድሮ የጐርፍ አደጋ ሕይወታቸው ያለፈ ሰዎች ቁጥር የቀነሰ ቢመስልም፣ በተለይ በንብረት ላይ ግን በብዙ ሚሊዮን ብር የሚገመት ንብረት መውደሙን ከመግለጽ ባለፈ፣ እርግጠኛውን አኃዝ ማስቀመጥ እንዳልተቻለ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የእሳትና ድንገተኛ አደጋዎች መከላከልና መቆጣጠር ባለሥልጣን አስረድቷል፡፡

የባለሥልጣኑ የኮሙዩኒኬሽን ኦፊሰር አቶ ንጋቱ ማሞ ለሪፖርተር እንደገለጹት፣ በተለይ በንብረት ላይ ነሐሴ 19 ለ20 አጥቢያ 2006 ዓ.ም. ሌሊቱን ሲጥል ባደረው ዝናብ በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ሪቼ አካባቢ በመኖሪያ ቤቶች ላይ ጉዳት ደርሷል፡፡ እንደ ኦፊሰሩ ገለጻ የጐርፍ አደጋ በተደጋጋሚ በሚያጠቃቸው አፍንጮ በር፣ አምባሳደር፣ ሲኤምሲ፣ አዋሬ፣ ቀጨኔ፣ ኦሎምፒያ፣ ስድስት ኪሎ ዩኒቨርሲቲ አካባቢ፣ ጳውሎስ ሆስፒታል ውስጥ፣ መነን አካባቢ፣ መካኒሳ፣ ካቴድራልና ጀሞ (23 መኖሪያ ቤቶች ላይ) የጐርፍ አደጋ ደርሶ ንብረት ማውደሙን አስረድተዋል፡፡

አቶ ንጋቱ ጨምረው እንደገለጹት፣ በክረምት ወቅት ብዙም የእሳት አደጋ የሚያሰጋ ባይሆንም፣ ነሐሴ 19 ቀን 2006 ዓ.ም. መርካቶ ጆንያ ተራ አካባቢ አደጋው ተከስቷል፡፡ በ2006 ዓ.ም. በተመሳሳይ ቦታ የደረሰው የእሳት አደጋ ለሁለተኛ ጊዜ መሆኑን የተናገሩት ኦፊሰሩ፣ አራት ሱቆች ብቻ መቃጠላቸውንና ግምቱ 360 ሺሕ ብር የሚሆን ንብረት መውደሙን ገልጸዋል፡፡ ስምንት ሚሊዮን ብር የሚገመት ንብረት መትረፉንም አክለዋል፡፡

ሙስና ለሶስት የሰነጠቃቸው ቡድኖች

$
0
0

ኢህአዴግ በጠመንጃ ኃይል ሥልጣን ላይ ፊጥ ካለ ድፍን 23 ዓመት ቆጠረ፡፡ ህወሃት/ኢህአዴግ በአንቀልባ አዝሎ ለሥልጣን ያበቃው ዛሬ አምርሮ የሚጠላው ሻዕቢያ ነው፡፡ ወያኔ እና ሻዕቢያ ውሃ በወንፊት እንቅዳ ባሉበት የፍቅር ዘመን እነኢሳያስ አፈወርቂ ኦፊሻል ባልሆነ መንገድ ጥሬ ሥጋ ለመቁረጥ በየሳምንቱ አዲስአበባ ይመላለሱ እንደነበር የቅርብ ሰዎች የሚያስታውሱት ነው፡፡

Muktar-300x142ዛሬስ፤ እነዚህ ሁለት ኃይሎች ለመጠፋፋት የሚፈላለጉ ሆነው ተፋጠዋል፡፡ የሚገርመው ወያኔ፤ የሻዕቢያ ጉዳይ አስፈጻሚ ሆኖ ሀገርን ያህል ነገር ማስገንጠሉን፣ አሰብን አስረክቦ ሀገሪቱን ያለወደብ ማስቀረቱን ጭምር እየረሳ የዛሬ ተቃዋሚዎችን ለምን ከሻዕቢያ ጋር ታያችሁ፣ገንዘብ ተቀበላችሁ እያለ በሀገር ክህደት ጭምር ለመክሰስ ሞራል አግኝቶ ሲወራጭ ማየት ነው፡፡ የትላንቱ የነጻነት ታጋዮች ለሕዝብ ነጻነትና ዴሞክራሲ ታግለናል እያሉ ከ20 ዓመታት ጉዞ በሁዋላ የተትረፈረፈ ነጻነቱን ለራሳቸው ሰጥተው ሌላውን ለመጨፍለቅና ትላንት ባወገዙት የደርግ መንገድ ለመጓዝ አላቅማሙም፡፡

ወደ ሰሞነኛ ጉዳይ እንመለስ ጄኔራል ባጫ ደበሌ አሜሪካን ሀገር ቤት ገዛ የሚል ገራገር ዜና ሰሞኑን በማህበራዊ ድረገጾች ሳነብ አባይን ያላየ ምንጭ ያደንቃል ብዬ በውስጤ አጉተምትሜያለሁ፡፡ የሌባው ቡድን መስረቅን እንደመብት ቆጥሮ በአዲስአበባ ከተማ ቀብረር ያለ ህንጻ በዘመድ አዝማዱ ሰም ሲገነባ ትንሽ እንኳን ሼም እንደሌለው ስትታዘብ ጄኔራሉ በአድራጎቱ አፍሮ ትንሽ ራቅ፣ ደበቅ ለማለት የመፈለጉን ነገር ታመሰግናለህ፡፡ የሌባው ቡድን 5ሺ ብር የማትሞላ ወርሃዊ ደመወዝ ይዞ ልጆቹን በውጪ ሀገር ውድ ት/ቤት ጭምር ሲያስተምር፣ ሚስቱ የሚሊየን ብሮች መኪና ስታሽከረክር፣ ባለቅንጦት ቪላ ገንብቶ ሲንጎማለል ስታይ ጄኔራሉ አንድ ቤት ቢገዛ ታዲያ ምን ይጠበስ ልትል ትችላለህ፡፡ እናም የመከላከያ ወታደሮችን ይጭነቃቸው እንጂ ጄኔራሎቹማ ዛሬ ቢጠሩዋቸው የማይሰሙ ቱጃሮች ሆነዋል፡፡ የሚገርመው ግን እነዚህ ጄኔራሎች ነገ ጥቅማቸውን የሚነካ ነገር ቢመጣ ብረት ላለማንሳታቸው ልማታዊ መንግሥታችንም እንኳን እርግጠኛ መሆን አለመቻሉ ነው፡፡ ኢህአዴግ ነፍሴም «ሙስናን እንዋጋለን» በሚል መፈክር ታጥሮ የሚኖረው ለዚህ ሳይሆን ይቀራልን?!

በአሁን ወቅት ገዥያችን ኢህአዴግ ለሶስት የመሰንጠቅ አዝማማያ እየታየበት ይገኛል፡፡

ቡድን አንድ የደረጀው የሌባ ቡድንን ያቀፈ ነው፡፡ ይህ ቡድን ከፍተኛ መንግሥታዊ ሥልጣኑን የተቆጣጠረ ስለሆነ ጥቅሙን ለማስጠበቅ ማንኛውንም የኃይል እርምጃ የሚወስድ፣ ጥቅሙ ሲነካ ወይንም ይነካል ብሎ ሲሰጋ ሰዎችን የሚያስር፣ የሚያሳድድ የጨካኞች ስብስብ ነው፡፡ እስከታችኛው ድረስ የራሱ መዋቅር የዘረጋና ብዙ ጀሌዎች ያሉት በመሆኑ ተጽእኖው የሰፋ ነው፡፡
ቡድን ሁለት ሟቹ ጠ/ሚኒስትር በአንድ ወቅት እንዳመነው ነገ ይቀናኝ ይሆናል ብሎ የተቀመጠ ተስፈኞች የተሰባሰቡበት ቡድን ነው፡፡ ይህ ቡድን የሌባው ቡድን ስላላስጠጋው አምርሮ እየተቃወመና ብሶቱን እየገለጸ ያለና እንደእስስት ገላውን የሚቀያይር ቡድን ነው፡፡ በተመቸው ጊዜ የሚደግፍ፣ ያልተመቸው ሲመስለው የሚቃወም እበላ ባይ የአደገኛ ሰዎች ስብስብ ነው፡፡ ይህ ቡድን በአመዛኙ በታችኛው እርከን ላይ ተከማችቶ የሚገኝ በመሆኑ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን በማባባስና በማወሳሰብ ዘወትር ቢወቀስም ምንም ለውጥ ማምጣት ያልቻለ ነው፡፡
ሶስተኛው የኢህአዴግ አባልም ደጋፊም ሆኖ እውነተኛ ዜጋ ሲሆን ሁለቱን ወገኖች የሚጠላ፤ ግን ተጋፍጦ ለመታገል አቅምና ድፍረት ያጣ ነው፡፡

በሒደት አንዱ ነጥሮ መውጣቱ የማይቀር ነው፡፡

( የእኔ የለጣፊው አስተያየት- አጠቃላይ ድርጅቱ የሚጠፋበት ጊዜ ሩቅ አይሆንም

ነጻነትን በማሳጣት ዜጎችን ለስቃይ፣ለእስራትና ለስደት የዳረገውን መንግስት ልናስወግደው ይገባል

$
0
0

ገዛኸኝ አበበበ ከኖርዌ ሌና)

BeFunky_BeFunky_CIMG1882.jpg

ወያኔ ኢህአዲግ የስልጣን ወንበሩን በሀይል ከተቆናጠጠበት ጊዜ ጀምሮ በስልጣን በቆየባቸው በሃያ ሶስት አመታቶች በየጊዜው በህዝባችን ላይ የሚያደርሰው ግፍ እና ጭቆና ከእለት ወደ እለት እየጨመረ መምጣቱ በአደባባይ የሚታይ እውነታ ሲሆን ከዚህም ጨቋኝና ገዳይ ስርዓት የተነሳ የሀገሪቷ ዚጓች  በሀገራቸው ላይ በሰላም መኖርና የነጻነትን ሀየር መተንፈስ በማይችሉበት ክፉ ሁኔታ ውስጥ ይገኛሉ::ለሰው ልጅ ነጻነቱ እየተገፈፈና መብቱ እየተረገጠ እንደ መኖርን የመሰለ አስቀያሚ ህይወት ያለ አይመስለኝም::ስለዚህ ነው በአሁኑ ጊዜ ከማንኛውም ጊዜ በተለየ መልኩ በሀገራችን ኢትዮጵያ  ገበሬው፣  ተማሪው፣  ፣ አስተማሪው ፣ ነጋዲው፣ ጋዜጠኛው ፣ ስፖርተኛው፣ ዘፋኙ፣ አርቲስቱ፣ ወዘተ……በማንኛውም እርከን ላይ የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች በሀገራቸው ላይ በነጻነት መኖርን ስላልቻሉ ባገኙት አጋጣሚ ሁሉ ሀገራቸውን ትተው እየወጡ በየጊዜው ለስደት ሲዳረጉ የሚታዩት::

ከሰሞኑ እንኳን እንደተመለከትነው አንድ ወር ባልሞላ ጊዜ ውስጥ በኢትዮጵያ ይገኙ የነበሩ ቁጥራቸው አስራ ሁለት የሚሆኑ ጋዜጠኞች የወያኔ መንግስት ስራቸውን እንደ ሚገባ እንዳይሰሩና በነጻነት አላንቀሳቅስ ስላላቸው ሀገራቸውን ጥለው ለስደት እንደተዳረጉ ሁላችንም የተመለከትነው ነገር ነው በዚህ አጭር ጊዜ ውስጥ ቁጥራቸ ቡዙ የሆኑ ጋዜጠኞች በአንድ ጊዜ ውስጥ ሀገራቸውን ጥለው ለስደት መዳረጋቸው ቡዞዎቻችንን የሚያስገርምና የሚያስደነግጥ ክስተት ሊሆን ይችላል ነገር ግን ለሰዎች ሁሉ የስደት ምንጭ የሆነው የወያኔ መንግስት ከስልጣኑ እስካልተወገደ ድረስ አፈና፣ እስራት፣ግድያው ከቀን ወደ ቀን እየተባባሰ በየትኛውም እርከን ላይ የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎች መቺም ቢሆን ለስደት መዳረጋቸው የማይቀር እውነታ ነው :.

ሌላው አንድ የታዘብኩት ነገር ሀገራቸውን ጥለው ለስደት ስለተዳረጉ ስለእነዚህ ጋዜጠኞች  በተለያዩ ሰዎች የተጻፉትን ጹሁፉችን ተመልክቻለው  አንዳንድ ሰዎችም የእነዚህ ጋዜጠኞች ከሀገር ለቁ መወጣት ስላልተዋጠላቸው የተለያዩ ትችቱችንና አስተያየቶችን ሲጽፉና ሲሰጡ ተመልክቻለው መቼም ቢሆን ማንኛውም ሰው በሀገሩ ላይ መማርን ፣መስራትንና፣ መኖርን የሚጠላ ሰው ያለ አይመስለኝም :: እነዚህን ጋዜጠኞች ከሌሎች ጋዚጠኞች ጋር እያነጻጸሩ ለምን እንደ እገሌ እዛው ሀገር ቤት ቁጭ ብለው አልታሰሩም ነበር ብሎ መፍረድ አግባብነት ያለው ፍርድ አይመስለኝም :: ማንም ሰው በሀገሩ በነጻነትና በሰላም መኖር ቢሆንለት ስደትን አይፈልግም :: ምክንያቱም ዜጓች በሀገራቸው በተረጋጋ ሁኔታ ለመኑር የሚያስፈልጋቸው  ዋንኛውና ቁልፉ ነገር ሰላም እና ነጻነት ነውና::ማንኛውም ሰው በሚኖርበት ሀገር በሚኖርበት ሰፈር ወይም አካባቢ እና በሚኖርበት ቤት ውስጥ ሳይቀር በሰላምና በነጻነት መኖርን ይፈልጋል:: ነጻነት በምንም ዋጋ ሊተመን የማይችል ትልቅ ጸጋ ነውና:: ሰላም እና ነጻነት በሌለበት ሀገር የሚኖሩ ዜጓች፣   መብታቸው ይረገጣል ፣ ነጻነታቸው ይታፈናል  ዜጓች ለእስር፣ ለሞት፣ እና ለስደት ይደጋሉ::በሀገራችን ኢትዮጵያ የምናየውም በእነዚህ አስራ ሁለት ጋዜጠኞች ላይ የደረሰው ይሄው ነው::

 እንደ አለመታደል ሆኖ ሀገራችን ኢትዮጵያም በአለም ላይ ካሉት ሀገራት በግንባር ቀደምነት  የሰው ልጆች ነጻነታቸውን እና መብታቸውን ከሚገፈፉበት ሀገር ተርታ እንደምትገኝና የሀገሪቷ ዜጓች በጨቋኙ ገዥ ስርዓት ነጻነታቸውን ተገፈው ባሪያ ሆነው የሚኖሩበት ሀገር እንደሆነች በየጊዜው ከሚወጡ አለም አቀፍ ሪፖርቶች መረዳት ይቻላል::::

 ዜጓች በከፍተኛ ሁኔታ ለስደት እየተዳረጉ ባሉበት በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ ሕዝብ ላይ የሚደረገው አፈና፣ እስራት እና ግድያው በከፍተኛ ሁኔታ ተባብሶ የሚገኝ ሲሆን ይህም በገሃድ እየታየ ያለ እውነታ ነው :: በእነዚህ ሃያ ሶስት አመታቶች በፋሺስቱ የወያኔ ቡድን ነጻነቱ እየተገፈፈና መብቱ እየተረገጠ ያለው የኢትዮጵያ ሕዝብም ከእንግዲህ ወዲህ ይሂን የወረበሎች ቡድን እሽሩሩ እያሉ የመኖር አቅም ያለው አይመሰልም :.: በአሁኑ ጊዜ ከየአቅጣጫው ከሚሰሙ ነጻነት ናፋቂ የኢትዮጵያኖቸ ሕዝብ ጩኸት ድምጽ መረዳት እንደሚቻለው ሕዝባችን ለወያኔያዊ አንባገነን ስርዓት መገዛትን የጠላበትና ከመቺውም ጊዜ በተለየ መልኩ እምቢ አሻፈረኝ ብሎ ነጻነቱን ለማስመለስ በአንድነት ለመቋም የተነሳበት ዘመን ላይ የደረሰን በሚያስመስል መልኩ ከየቦታው የሚሰማው የነጻነትና የሰላም ናፋቂዎች የጀግንነት ድምጽ ምስክር ነው::

በቅርቡ እንኳን እንደምናየው የግንቦት 7 የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ ዋና ጸሀፊ የአቶ አንዳርጋቸው ጽጌን ከየመን ታግተው በወያኔ እስር ቤት ታስረው በግፍ እየተሰቃዩ እንዳለ ይታወቃል የነጻነት ታጋዩ አቶ አንዳርጋቸው በወያኔ ሴራ ከየመን ታግተው በወያኔ እጅ ላይ መውደቃቸው ከተሰማ ጊዜ ጀምሮ የኢትዮጵያ ሕዝብ የወያኔን አውሬነት በይበልጥ በመረዳት ከዳር እስከ ዳር በአንድነት መቋሙን እያስመሰከረ ሲገኝ የፖለቲካ ግለቱም ጨምሮ የአረመኔው የወያኔን ቡድን በከፍተኛ ሁኔታ አርበድብዶት እንደሚገኝ ወያኔ ከሚሰራው ስራና ከሚያደርጋቸው ድርጊቷች ማወቅ ይቻላል::የአቶ አንዳርጋቸውን መታሰር ተከትሎ  እየከረረ ያለውን የሕዝብን ቁጭትና ቁጣ ለማጥፋት በሚያስመስል መልኩ ይኼ አረመኔው መንግስት በአሁኑ ጊዜ በሀገር ቤት በሰላማዊ መንገድ ለመብታቸው እና ለኢትዮጵያ ሕዝብ ነጻነት በህጋዊ መንገድ እንኮን ሳይቀር እየታገሉ ያሉትን ሰዎች ከየመንገዱ እየለቀመ እስር ቤት አስገብቶ እያሰቃያቸው እንዳለ ይታወቃል ::ይህንንም ተከትሎ  ሁላችንም እንደምናውቀው  የአንድነት ፓርቲ ሥራ አስፈጻሚ አባልና ሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ሀብታሙ አያሌው፣ የፓርቲው ምክር ቤት አባል አቶ ዳንኤል ሺበሺ፣ የአረና የሕዝብ ግንኙንት ኃላፊ አቶ አብረሃ ደስታና የሰማያዊ ፓርቲ ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባዔ አቶ የሸዋስ አሰፋን ጨምሮ ሌሎችም እጅግ ብዙ ለየጻነታቸው የሚታገሉ ኢትዮጵያን ወገኖቻችን  የወያኔ መንግስት በግፍ  አስሯቸው እያሰቃያቸው እንደሚገኝ ይታወቃል::

ይኼ መንግስት እሱን  የሚቃወሙትን ሰዎችንና በድፍረት እየተጋፈጡት ያሉትን የፖለቲካ መሪዎች አአሸባሪ የሚል የታርጋ ስም እየለጠፈላቸው ወደ እስር ቤት መወርወር የተጠናወጠው ክፉ ባህሪው ሆኖል:: የፖለቲካ መሪዎችንና የፖለቲካ ሰዎችን ማፈንና እየያዙ ወደ እስር ቤት መወርወር ይበልጥኑ ትግሉን እያከረረውና የኢትዮጵያን ሕዝብ ይበልጥኑ ለነጻነቱ በመታገል ለድል እያነሳሳው  ነው እንጂ ፈጽሞ ከትግል ወደ ኋላ እይመለሰው እንዳይደለ የወያኔ ባለስልጣኖች ጠንቅቀው ሊያውቁት የሚገባቸው ነገር ይመስለኛል:: የኢትዮጵያ ሕዝብ ነጻነትን ተጠምቷል ::Freedom is more than food  በአሁኑ ሰአት በሀገር ቤትም ሆነው በሰላማዊ መንገድ እየታገሉ ያሉ የፖለቲካ ድርጅቶች ይሁኑ ወይም በውጭ ሆነው በሁለገብ ትግል እየታገሉ ያሉ የፖለቲካ ድርጅቶች አላማቸውም ሆነ ጥያቄያቸው አንድ ነው የስልጣን ወይም የገንዘብ ሳይሆን የነጻነት ጥያቄ ነው :: የኢትዮጵያ ሕዝብ ነጻነት ያስፈልገዋል   ::እኛም  ሰላምና ነጻነት የናፈቀን ህዝቦች መብታችንን ለማስከበር ለነጻነት ከሚታገሉ ድርጅቷች ጎን በመቆም ለነጻነታቸው ሲታገሉ  በወያኔ አንባገነን ትህዛዝ ወደ እስር እየተወረወሩ እና በግፍ እየተሰቃዩ ላሉ ወገኖቻችን  ከመንኛውም ጊዜ በተለየ መልኩ ሀገራዊ ስሜት ተሰሞቶን ልንጮህላቸውና የእነሱንም ፈለግ በመከተል ከሁለት አስርት አመታት በላይ የዜግነት መብታችንና እየረገጠና ነጻነታችንን እያፈነ ህዝባችንን ለስደት እያደረገ ያለውን ያለውን ይኼን ሰይጣናዊና አረመናዊ ስርዓት በማንኛውም መንገድ በመታገል፣እውነተኛ ሰላምና ነጻነት በኢትዮጵያ ምድራችን እንዲመጣ ለማድረግ የወያኔን መንግስት ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ዳግም እንዳይነሳ  አከርካሪውን ሰብሮ መጣል  ይጠበቅብናል እላለው::የዜጎች ነጻነት ማጣት ፣መሰቃየት፣ መታሰርና መሰደድ ግድ ብሎን እያንዳንዳችን ትግላችንም ሆነ አላማችን በእውነተኛ የነጻነት ትግል በመነሳት የወያኔን መንግስት ጥሎ ነጻነትን ለመቀናጀት በኢትዮጵያዊ  ስሜትና ተነሳሽነት ከሆነ ድልን የምንቀድጅበት ቀን ሩቅ መስሎ አይታየኝም::

  ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ !!!
gezapower@gmail.com

የኢትዮጵያ ሕዝበ ሙስሊም ሊያውቀው የሚገባ ጥልቅ ምስጢር (ከትህዴን የተላለፈ ቪድዮ)

$
0
0

የኢትዮጵያ ህዝበ-መስሊም ሊያወቀው የሚገባው ትልቅ ምስጢር!!
- የኣል ኣህባሽ ፤ ኣልቃይዳ ፤ ኣል-ሸባብ፤ ወደ ኢትዮጵያ እንዴት ገቡ? በማንስ ገቡ?
- ኢትዮጵያውያን መስሊሞች ለምን ከሳውዲ ኣገር ተባረሩ? ለምንስ የሌላ ኣገር ዜጎች ኣልተባረሩም?
- የኢትዮጵያውያን የእስልምና መብት ጥያቄ ምንድ ነው? ከየትስ መጣ? ከየት ወዴት እየሄደ ነው?
- እስልምና ምንድ ነው?
- ወሃቢዝም ምንድ ነው? ምን ማለት ነው?
የሚሉና ሌሎች በርካታ ጥያቄዎች በዚህ ቃለ-መጠይቅ ተካትተዋል። ህዝበ-መስሊዩም ሊያወቀው የሚገባው ትልቅ ምስጥር!!


የኢትዮጵያ ሕዝበ ሙስሊም ሊያውቀው የሚገባ ጥልቅ ምስጢር (ከትህዴን የተላለፈ ቪድዮ)

Viewing all 15006 articles
Browse latest View live