Quantcast
Channel: Ethiopian News | ዘ-ሐበሻ | Latest News Provider | News For All
Viewing all 15006 articles
Browse latest View live

የግንቦት 7 ሕዝባዊ ስብሰባዎች በዓለም ሃያ ስድስት ታላላቅ ከተሞች

0
0

ግንቦት 7: የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ በመላው ዓለም ላይ ከሚገኙ አባላት፣ ደጋፊዎቹና በአጠቃላይ ከኢትዮጵያውያን ጋር በወቅታዊ ሁኔታዎች ላይ ለመመካከር ዝግጅቱን አጠናቋል።

በዚህም መሠረት ከዚህ በታች በተዘረዘሩት 26 የዓለም ታላላቅ ከተሞች ሕዝባዊ ስብሰባዎችን ተጠርቷል።

images (2)በላስቤጋስ ዩ ኤስ አሜሪካ ረቡስ ኦገስት 27 ቀን
በሂውስተውን ዩ ኤስ አሜሪካ ቅዳሜ ኦገስት 30 ቀን
በአትላንታ ዩ ኤስ አሜሪካ እሁድ ኦገስት 31 ቀን
በዋሺንግተን ዲሲ ዩ ኤስ አሜሪካ እሁድ ኦገስት 31 ቀን
በቦስተን ዩ ኤስ አሜሪካ እሁድ ኦገስት 31 ቀን
በሎስ አንጀለስ ዩ ኤስ አሜሪካ ቅዳሜ ሴፕተምበር 6 ቀን
በሳንቲያጎ ዩ ኤስ አሜሪካ እሁድ ሴፕተምበር 7 ቀን
በቶሮንቶ ካናዳ እሁድ ኦገስት 31 ቀን
በካልጋሪ ካናዳ ሴፕቴምበር 1 ቀን
በደርባን ደቡብ አፍሪቃ እሁድ ኦገስት 31 ቀን
በጆሃንስበርግ ደቡብ አፍሪቃ እሁድ ኦገስት 31 ቀን
ቬሪኒንፍ ደቡብ አፍሪቃ እሁድ ኦገስት 31 ቀን
ሩስተምበርግ ደቡብ አፍሪቃ እሁድ ኦገስት 31 ቀን
ፍራክፈርት ጀርመን ቅዳሜ ኦገስት 30 ቀን
ሙኒክ ጀርመን እሁድ ኦገስት 31 ቀን
ሄልሲንኪ ፊንላንድ ቅዳሜ ኦገስት 30 ቀን
አምስተርዳም ኒዘርላንድስ ቅዳሜ ሴፕተምበር 13 ቀን
ኦስሎ ኖርዌይ እሁድ ኦገስት 31 ቀን
ለንደን እንግሊዝ ቅዳሜ ሴፕተምበር 6 ቀን
ስቶክሆልም ስዊድን ቅዳሜ ሴፕተምበር 6 ቀን
ፐርዝ አውስትራሊያ እሁድ ኦገስት 31 ቀን
ሜልቦርን አውስትራሊያ እሁድ ሴፕቴምበር 7 ቀን
ቴላቪቭ እስራኤል ሐሙስ ሴፕቴምበር 11 ቀን
ብራሰልስ ቤልጂየም እሁድ ሴፕቴምበር 14 ቀን
ኦክላን ኒዩ ዚላንድ እሁድ ኦገስት 31 ቀን
ሲኡል ደቡብ ኮርያ እሁድ ኦገስት 31 ቀን
በእነዚህ ስብሰባዎች ሁሉ የንቅናቄዓችን ዋና ፀሐፊ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ሥራዎች ይወሳሉ። ወያኔን ማስወገድ በሚቻልበት ስልቶች ላይ ውይይት ይደረጋል። እስከዛሬ ድረስ ንቅናቄዓችንን ለመቀላቀል የተቸገራችሁ ወገኖች ይህንን አጋጣሚ እንድትጠቀሙበት ጥሪ እናደርጋለን። በማናቸውም ምክንያት አባል ሳይሆን ደጋፊ መሆን ለምትፈልጉ ወገኖቻችንን የደጋፊዎች ምዝገባ ሥርዓት አዘጋጅተናል፤ እድሉን ተጠቀሙበት።

ኑ! ኢትዮጵያ አገራችንን፣ ኢትዮጵያዊ ወገናችንን እና ራሳችን ነፃ ለማውጣት እና በሀገራችን ፍትህ እንዲሰፍን ለማድረግ የሚደረገውን ትግል ይቀላቀሉ። ከዘወትር የህሊና ወቀሳ ይገላገሉ። ለዚህ ትግል ሁሉም የሚያበረክተው ነገር አለ። ስለሆነም በአቅራቢያዎ ወደሚደረገው የግንቦት 7 ስብሰባ ይምጡ፤ ጥያቄዎች ካልዎት ይጠይቁ።

አሁን ወሳኝ የትግል ምዕራፍ ላይ እንገኛለን። ትግላችን ሶስት የትግል ስልቶችን ያስተባበረ ነው – ሕዝባዊ ተቃውሞ፣ ሕዝባዊ እምቢተኝነት እና ሕዝባዊ አመጽ። ትግላችን በአገር ውስጥም ከአገር ውጭም ነው።

በውጭ አገራት የሚገኙ ኢትዮጵያዊያን ከድጋፍ ሰጪነት ወደ ተግባራዊ ተሳትፎ የተሸጋገሩበት ወቅት ነው። ይህ ተጠናክሮ ሊቀጥል ይገባዋል። የወያኔ ድርጅቶችና የወያኔ ሹማምንት በየትኛው አገር ተዝናንተው እንዲኖሩና እንዲነግዱ አንፈቅድላቸውም። በእነዚህ ስብሰባዎች ስለዚህ ጉዳይ ይመከራል።

ኢትዮጵያዊያን ወጣቶች ለኢትዮጵያ ክብርና ነፃነት ሕይወታቸውን ለመሰዋት ተነስተዋል። በእነዚህ ስብሰባዎች የአርበኛ ወጣቶቻችንን ጥረት እንዘክራለን። ሺዎች እንዲቀላቀሏቸው ጥሪ እናደርጋለን። በሁሉም ስብሰባዎች በአገር ውስጥም በውጭ አገርም የሚገኝ ኢትዮጵያዊ ወጣት ትግሉን እንዲቀላቀል ጥሪ ይደረግለታል።

በሁሉም ስብሰባዎች ለኢትዮጵያ የመከላከያ ሠራዊት አባላት ጥሪ ይደረጋል። የሠራዊቱ መሪዎች የፋሽስት ወያኔ ባለሟሎች ቢሆኑም ሠራዊቱ ግን ከኢትዮጵያ አብራክ የወጣ ኢትዮጵያዊ ነው። ሠራዊቱ የወያኔ መጠቀሚያ ከመሆን የነፃነት ታጋዮችን እንዲቀላቀል፤ ያ ካልተቻለም ለወያኔ ሥልጣን እንዳይሞት፤ ወገኑን እንዳይገል ጥሪ ይደረግለታል።

መጥተው የእነዚህ ታሪካዊ ስብሰባዎች አካል ይሁኑ።

ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!!!


ከውጭ የተላከ ያልተመዘገበ ገንዘብ /የሐዋላ ቅሸባ

0
0

ddከሚሊዬን ዘአማኑኤል እንደ ዓለም ባንክ መረጃ መሠረት በግምት 30 ሚሊዩን አፍሪካዊያን በAለም ላይ ተሰደው ይገኛሉ፡፡ የአፍሪካውያን ስደተኞች ቁጥር በሚቀጥሉት Aስርት ዓመታት ውስጥ እንደሚጨምር ህዝበ ፅንፍ ተመራማሪዎች ይተነብያሉ፡፡ በአፍሪካ በሚሊዩን የሚቆጠሩ ቤተስቦች ባህር ማዶ ከሚኖሩ ዘመዶቻቸው በሚላክ የውጭ ሐዋላ ወይም ገንዘብ Eየተዳደሩ እንደሚኖሩ ይታመናል፡፡ በ2010 እኤአ  በክፍለ አህጉሩ የውጭ ሐዋላ ፍሰት በአለፉት ሃያ አመታት ውስጥ አራት እጥፍ Eንደአደገ Aጥኝዎች ይገምታሉ ማለትም 40 ቢሊዩን ዩኤስ ዶለር ይገመታል ይህም (ከብሔራዊ ዓመታዊ ጠቅላላ ምርት 2.5 በመቶ) ድርሻ እንዳለው ጠበብት ይገልፃሉ፡፡ለአፍሪካ አህጉር የውጭ ቀጥተኛ Iንቨስትመንት አንደኛ ደረጃ የገቢ ምንጭ ሲሆን ማለትም ከአጠቃላይ የውጭ መዋለ ንዋይ ፍስት ዋነኛ ድርሻ አለው፡፡ቀጥሎ የዓለም ዓቀፍ የውጭ ሐዋላ ፍሰት በክፍለ አህጉሩ ሁለተኛ ደረጃ የገቢ ምንጭ ድርሻ አስመዝግቦ ይገኛል፡፡በንፅፅር ሲታይ የውጭ ሐዋላ የገቢ ምንጭነት ከውጭ እርዳታ እንደሚበልጥ የዓለም ባንክ መረጃ ያረጋግጣል፡፡በክፍለ አህጉሩ ሦስተኛ ደረጃ የገቢ ምንጭ ድርሻ ያለው የውጭ እርዳታ ነው፡፡  –- ––[ሙሉውን ለማንበብ እዚህ ይጫኑ]———

Health: የጉበት በሽተኛ ነኝ፣ በምን መልኩ በዕድሜ መቆየት እችላለሁ?

0
0

የጉበት በሽተኛ መሆኔ ታውቆ ህክምና መከታተል ከጀመርኩ ወራቶች አለፉኝ፡፡ ሆኖም ስለ በሽታው ያለኝ ግንዛቤ ዘወትር የሚከሰትብኝን ድንገተኛ አካላዊ ለውጥ እና የህመም ስሜት እየረበሸኝ ይገኛል፡፡ አሁን እንደሰማሁት ከሆነ ደግሞ ብዙ አይነት የጉበት ቫይረሶች ይገኛሉ፡፡ እነዚህ አይነቶች ምን እንደሆኑ የማውቀው ነገር የለም፡፡ ሐኪሞቼ ከሰጡኝ የጥንቃቄ ምክር ውጭስ እንዴት የህመም ስሜት ሊፈጠርብኝስ ቻለ? በእርግጥ ግን ይህ በሽታ ይድን ይሆን? እባካችሁ ስጋቴን አቅልሉልኝ፡፡
እዮብ ነኝ

hepatitis-s1-liver-hepatitis-virus
ውድ አንባቢያችን ስጋትህ ግልፅ ነው፡፡ ሆኖም ያንተ የጉበት ቫይረስ ችግር የትኛው አይነት እንደሆነ ለማወቅ ዝርዝር ጉዳዮችን አልፃፍክልንም፡፡ ሆኖም በሽታው በአጠቃላይ የመዳን ዕድሉ ከፍተኛ ነው፡፡ ይህን ቫይረስ በተመለከተ ግንዛቤ ከማስጨበጥ የዘለለ እርዳታ ልናደርግልህ ባንችልም እነሆ ስለ ጉበትና የጉበት ቫይረሶች እንደሚከተለው ጠቅለል አድርገን ልናጫውትህ ወደድን፡፡
ጉበት የተባለው የሰውነት አካል ከሆድ ዕቃዎች ውስጥ ትልቁና ውስብስብ ስራ ከሚሰሩት ዋና ዋና የሰውነት ክፍላችን ውስጥ አንዱ ነው፡፡
ጉበት የሚገኘው በቀኝ በኩል ከጎድን አጥንታችን ዝቅ ብሎ ሲሆን የሚሰራቸውን ስራዎች በጥቅሉ ስንመለከት፡-

- የምንመገበውንና የምንጠጣውን ወይም በሰውነታችን ውስጥ የሚመረተውን ጎጂ የሆነ ነገር በማስወገድና ጎጂ ወደ አልሆነ ሁኔታ በመቀየር በደም አማካኝነት በኩላሊት አድርጎ ከሽንት ጋር ወይም በአንጀት በኩል ከአይነ ምድር ጋር እንዲወገድ ለማድረግ ይረዳል፡፡
- ምግብ ከተፈጨ በኋላ በውስጡ ያለውን ንጥረ ነገር ወደ ፕሮቲን፣ ካርቦሃይድሬትና ፋት ከመቀየርም በላይ ሰውነታችን ያልተጠቀመውን የኃይል መጠን በጉበት ውስጥ በሚቀመጥ መልኩ ይዞ የሰውነት ስኳር ዝቅ በሚልበት ወቅት የኃይል ሰጪ ምንጭ በመሆን ያገለግላል፡፡
- 50 በመቶ የሚሆነው ሰውነት የሚያስፈልገው የኮሌስትሮል መጠን በጉበት አማካኝነት ሲመረት የተቀየረው 50 ፐርሰንት ደግሞ ከምንመገበው ምግብ የምናገኘው ይሆናል፡፡ በጉበት ከሚመረተው ኮሌስትሮል ውስጥ 80 ፐርሰንት የሚሆነው ሀሞት ለመስራት ሲያገለግል የተቀረው ደግሞ የተለያዩ በሰውነታችን ውስጥ አስፈላጊ የሆኑትን ሆርሞኖች ለመስራት ይጠቅማል፡፡ በተጨማሪም በማንኛውም ሴል ውስጥ መገኘት ያለበት እንደመሆኑ ወሳኝ ሚናን ይጫወታል ማለት ነው፡፡

- በተጨማሪም የተለያዩ አስፈላጊ የሆኑ ንጥረ ነገሮችና ፕሮቲኖች በተለይም ደግሞ ደም እንዲረጋ የሚያግዙ በርካታ ንጥረ ነገሮችን በማምረት መሰረታዊ የሆነ ጥቅም ይሰጣል፡፡

ታዲያ ጉበቱ ይሄንን ያህል ጥቅም ካለው የጉበት መጎዳት ምን ያህል ችግር ሊያስከትል እንደሚችል ከወዲሁ መገመት አያዳግትም፡፡ ለዛሬ በዋነኛነት የምንመለከተው የጉበት መቆጣት ሄፖታይተስ /hepatitis/ ሲሆን ይሄንን ጉዳይ በዝርዝር እንመለከታለን፡፡
Hepatitis የተባለው የጉበት በሽታ በተለያየ ምክንያት ሊፈጠር የሚችል የጉበት የመቆጣት ሁኔታ ነው፡፡ ለዚህ ችግር በዋነኛነት እንደ መንስኤ የሚጠቀሱት የሄፖታይተስ ቫይረስ የሚባሉ አምስት የተለያዩ የቫይረስ አይነቶች ሲሆኑ፤ ከእነዚህ ቫይረሶች በአንዱ ወይንም ከዛ በላይ በአንድ ጊዜ የመጠቃት ሁኔታ ሊያጋጥም ይችላል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ ሌሎች እንደ የአልኮል መጠጥና መድሃኒት የመሳሰሉ ነገሮች ተመሳሳይ ችግር ሊያስከትሉ ይችላሉ፡፡
እነዚህ አምስት አይነት አሉ ያልናቸው የሄፖታይተስ ቫይረሶችን ስንመለከት፡

- ሄፖታይተስ ኤ ቫይረስ፡- በዋነኛነት የሚተላለፈው በንፅህና ጉድለት ሲሆን ይሄም ከተበከለ ምግብ/መጠጥ ወይንም እጅ ካለመታጠብ ከሰው ሰው በቀላሉ ሊተላለፍ የሚችል ሁኔታ ነው፡፡
- ሄፖታይተስ ቢ ቫይረስ፡- ይህ የቫይረስ አይነት በዋነኛነት የሚተላለፈው በደምና በደም ውጤቶች እንዲሁም ሌሎች የሰውነት ፈሳሽ ንክኪ በሚሆንበት ጊዜ ሲሆን ከእናት ወደ ልጅ፣ ያልተመረመረ ደም በመውሰድ፣ በግብረ ስጋ ግንኙነት ወቅት እንዲሁም በዲያሊስስ ጊዜ ሊተላለፍ የሚችል ሁኔታ ነው፡፡
- ሄፖታይተስ ሲ ቫይረስ፡- ይህ የቫይረስ አይነት ከሄፖታይተስ ቢ ቫይረስ ጋር ተመሳሳይ የመተላለፊያ መንገድ ቢኖረውም ከግብረ ስጋ ግንኙነትና ከእናት ወደ ልጅ የመተላለፍ እድሉ በተወሰነ መልኩ ይቀንሳል፡፡
ሄፖታይተስ ዲ ቫይረስ፡- ይህ ቫይረስ ሄፖታይተሲስ ባላቸው ሰዎች ላይ ብቻ የሚከሰት ሲሆን መተላለፊያ መንገዶቹ በመሰረቱ ከሄፖታይተስ ቢ እና ሲ ጋር ተመሳሳይ ሆኖ እናገኘዋለን፡፡
- ሄፖታይተስ ኢ ቫይረስ፡- ከሄፖታይተስ ኤ ጋር ተመሳሳይ የመተላለፊያ ባህሪ ያለው ነው፡፡
በመሰረቱ የጉበት መቆጣት፡- ከ6 ወር በታች የሚቆይ የጉበት ችግር
- ረጅም ጊዜ የሚቆይ /chronic hepatitis/፡- 6 ወርና ከዛ በላይ የሚቆይ የጉበት ችግር በመባል ይታወቃሉ፡፡ ከዚህም በመነሳት በቫይረስ አማካኝነት የሚፈጠረውን ‹‹A cute hepatitis››እና በተለያየ ሳቢያ ሊከተል የሚችለውን ‹‹Chronic hepatitis›› ሰፋ አድርገን እንመለከታለን፡፡
Acute viral hepatitis:- ይህ ሁኔታ ከላይ እንደተጠቀሰው በቫይረሶች ሳቢያ የሚመጣ ሁኔታ ሲሆን በአብዛኛው ጊዜ ሲታይ በአፋጣኝ የሚከሰትና ለመጥፋትም ብዙ ጊዜ የማይፈጅበት ሁኔታ ነው፡፡

በዚህ ጊዜ ከሚከተሉ ስሜቶች ውስጥ የምግብ ፍላጎት መቀነስ፣ ማቅለሽለሽና ማስመለስ፣ ትኩሳትና፣ የአጥንት መገጣጠሚያ ህመም መሰማት፣ እንዲሁም አጠቃላይ የህመም ስሜት በጥቂቱ ይጠቀሳሉ፡፡ ይህ ሁኔታ በአፋጣኝ ከተከሰተ ከትንሽ ቀናት በኋላ የአይንና የቆዳ ቀለም ቢጫ መሆን፣ የሽንት ቀለም መጥቆርና የአይነ ምድር ቀለም መንጣት ይከተላልና በአብዛኛው ጊዜ ከላይ የተጠቀሱት ምልክቶች ጠፍተው የጤንነት ስሜት መሰማት ይከተላል፡፡

ነገር ግን የሰውነት/የአይን ቀለም ቢጫ መሆን ይቀጥልና ከ1-2 ሳምንት ባለው ጊዜ ውስጥ ከፍተኛ ደረጃ በመድረስ ከ2-4 ባሉት ሳምንታት ውስጥ ሁኔታዎች እየተሻሻሉ የአይንና የቆዳ ቀለም ወደ ቀድሞው ይመለሳል፡፡ ከዚህ በተጨማሪም በቀኝ በኩል ጎድን አጥንት ስር የህመም ስሜት መሰማትና አጠቃላይ ሰውነት ማሳከክ በተደጋጋሚ የሚታዩ ስሜቶች ናቸው፡፡

በአብዛኛው ይህ የጉበት በሽታ የሚታወቀው በሚያስከትለው የህመም ስሜቶች ሳቢያ ቢሆንም የተለያየ የደም ምርመራዎችን ማድረግና ሁኔታውን ማጣራት/ማረጋገጥ አስፈላጊውን እርምጃ ለመውሰድ ተገቢ ይሆናል…

አጣዳፊ ያልሆነና ረጅም ጊዜ የሚቆይ
ሄፓታይተስ /chronic hepatitis/

ይህ ክሮኒክ ሄፖታይተስ ከአጣዳፊው ሄፖታይተስ ባነሰ ሁኔታ የሚታይ ቢሆንም ለወራትና ለዓመታት ምንም አይነት ስሜትና ችግር ሳያስከትል መቆየት የሚችል ነገር ግን በአንድ አንድ ሁኔታዎች ደግሞ ለከፍተኛ የጉበት መጎዳትና ብሎም ለሞት ሊዳርግ የሚችል ሁኔታ ነው፡፡
በአብዛኛው ለዚህ ሁኔታ የሚዳርገው የሄፖታይተስ ሲ ቫይረስ ሲሆን 75 ፐርሰንት የሚሆነው በዚህ ቫይረስ የሚከሰተው የጉበት ችግር ወደ ክሮኒክ ሄፖተይተስ የመቀየር ባህሪ ያሳያል፡፡ የሄፖታይቲስ ቢ ቫይረስም በተለይ ከሄፖታይተስ ዲ ቫይረስ ጋር በመሆን በተወሰነ መልኩ ይሄንን ሁኔታ ሊያስከትሉ፣ በአንፃሩ የሄፖታይቲስ ኤ እናኢ ቫይረስ ይሄንን ችግር የማስከተል ዕድል የላቸውም ማለት ይቻላል፡፡

ከዚህም በተጨማሪ ሌሎች የተለያዩ የጉበት በሽታዎች፣ መድሃኒትና አልኮል መጠጥ ለዚህ ሁኔታ ሊያጋልጡን ይችላሉ፡፡

በአብዛኛው ጊዜ ክሮኒክ ሄፖታይተስ ስሜት አልባ የሆነ የህመም አይነት ቢሆንም ሊያስከትል ከሚችለው ስሜቶች ውስጥ የምግብ ፍላጎት መቀነስ፣ ድካምና አጠቃላይ የህመም ስሜት መሰማት፣ አነስተኛ ትኩሳት፣ አይንና ቆዳ ቢጫ መሆን እንዲሁም በቀኝ በኩል የህመም ስሜት መሰማት ናቸው፡፡ ከዚህ በተጨማሪም ከጊዜ በኋላ ጉበት መጎዳቱን የሚያመላክቱ እንደ ጣፊያ ማበጥና፣ የሰውነት ውሃ መቋጠርና ማበጥ ተከትሎ ሊታይ ይችላል፡፡ በአብዛኛው ይህንን ሁኔታ ለማወቅና ለማጣራት ከደም ምርመራ ባሻገር ከጉበት ላይ ናሙና በመውሰድ መመርመር ተመራጩ የምርመራ አይነት ናቸው፡፡
ከላይ እንደተመለከትናቸው የተለያዩ አይነት ሁኔታዎች የጉበት ጉዳትን ሊያስከትሉ እንደመቻላቸው መጠን ተገቢውን ጥንቃቄ አስቀድሞ ማድረግ ተገቢ ይሆናል፡፡
- አጠቃላይ ንፅህናን መጠበቅና ምግብ ከመብላት ወይንም ከማዘጋጀት በፊት እጅን መታጠብ አስፈላጊና መሰረታዊ ነው፡፡
- የደምና የደም ውጤቶች እንዲሁም የሰውነት ፈሳሽ ንክኪ ሊፈጥሩ የሚችሉ የተለያዩ ሁኔታዎችን ከግምት በማስገባት እንደየፈርጁ መከላከል፣ ለምሳሌ በሆስፒታል ውስጥ ጓንት መጠቀም፣ ንፁህ/አዲስ መርፌ ብቻ መጠቀም፣ ደም ከመለገስ በፊት ማጣራት፣ የግብረ ስጋ ግንኙነት ጊዜ ኮንዶም መጠቀም የመሳሰሉት በጥቂቱ ይገለፃሉ፡፡
- በእርግዝና ወቅት የደም ምርመራ ማድረግና ከእናት ወደ ልጅ እንዳይተላለፍ አስፈላጊውን እርምጃ መውሰድ፡፡
- ለሄፖታይተስ ኤ እና ቢ ቫይረሶች የተዘጋጀ ክትባት እንደ አስፈላጊ መውሰድ
ማንኛውም ተመሳሳይ የሆነ የህመም ስሜት በሚሰማ ወቅት የህክምና ባለሙያ ጋር በመሄድ አስፈላጊውን ምክርና የህክምና አገልግሎት መቀበል ተገቢ ነው፡፡ በዚህም የተነሳ ታሞ ከመማቀቅ አስቀድሞ በመጠንቀቅ ከጉበት ህመም መራቅ ይቻላል፡፡

የጎረና ጉርና –ነዳላ (ሥርጉተ ሥላሴ)

0
0

ልብ አምላክ ዳዊት „ህግ ተላላፊዎችን ጠላሁ“ አለ።
ሱባኤውም ተጠናቀቀ – መልስ ይሰጥበት።

ከሥርጉተ ሥላሴ 25.08.2014 (ሲዊዘርላንድ – ዙሪክ)

ሥርጉተ ሥላሴ

ሥርጉተ ሥላሴ

ይድርስ ለጸሐፊ ጌታቸው ረዳ ካሉበት። እንደምን አሉ? ደህናነዎት ወይ። ደስ ሊለዎት የሚገባ ሊያሰተላልፉት የሚፈልጉትን መልዕክት በማስተላለፈዎት ሳይሆን እራሰዎትን ፈልገው ከመሸ በማግኘተዎት ነው። እንኳን ለዚህ አበቃዎት! አሻቅቦ መናገር ከመንፈሴ ዕድገት ውጪ ቢሆንም ልክን ማወቅ ከልክ የሚያድርስ ስለመሆኑ ተምሬ ስላደኩ አቻውን ዬፍላጎተዎትን እንሆ – ይረከቡኝ!

„ሆድ ያባውን ብቅል ያወጣዋል“ ወይ ዘመን ምኑን ጉድ ነው እዬዘለዘለ ያለው? እግዚአብሄር ይይልህ አይዋ ዘመን ምን አለበት ጉግልን ባትጋፋው?

የኔዎቹ እንዴት አላችሁልኝ። ጥያቄ ተጠዬቁ እስቲ። ደግሞ ብለው ብለው ላልጠፋው እህል እውሃ በነጭ ሀገር ብዕርና ብራና ስንቃቸው አብሾ ሆነ እንዴ?

አልኳችሁ ወዳጆቼ አጣደፉኝ። ስሄድ ካላሆነ ቦታ ገባሁ። ከዛንላችሁ ቀጥ ብዬ እርእሱን ይዤ ኤዲተር ካላው ወዳጄና ረጃጅም ትንተናዊ ጹሑፍ በማወጣት ወደ ዬሚታወቀው ኢትዮ ሚዲያ ጎራ ስል ተዛም ዝክንትሉ ብራና የለም። ያው እንደፈረደብኝ ተመልሼ እንደ ነገሩ ከብትክትኩ ጋር በባዕቱ መተያዬት አይቀር – ተያዬን። እርእሱና ፎቶው በቂ ነበር „የናዚ ኔት ወርክ“ ዘመናይ ነዎት —  ዖዬ!

ከዛ ደግሞ አነበብሽው? ምንስ ተሰማሽ መጣ? ስለ ወጣቶች „ላም ባልዋለበት ኩበት ለቀማ“ በመሆኑ ሰቀጠጠኝ። እኔ ለወጣት የነፃነት ትግሉ ቤተሰቦች ስስታም ነኝ። እንዲሁም ቀጥ ያለ አቋም ብቻ ላላቸው የመወያያ መድረኮችና ሙሁራንም እጅግ ቀናተኛ ነኝ።

በተረፈ እኔን በሚመለከት አደራ አበደች እንዳትሉኝ። ደስ አለኝ። እዬሳቅኩኝ ነበር የተያዬነው። በቃ የጠላት ጎራ መንፈስ እንዲህ በአንድ ጹሑፍ ትቅማጥ ሲይዘው ማዬት የምር ምኞቴ ነበር። ሆድ ዕቃው ወስፋቱ የተንጫጫ ሲገኝ አጋጠመ ነው። ለዚህ ነበር እኮ እኔ የጻፍኩት። በቃ!  ሁልጊዜ ፋሲካ የለምና እንደ ወትሮው መንፈስን ከአንድነት ኃይሉ ማፈናቀል ያልቸል ደካማ መሆኑ ደግሞ ተከታታይ መረጃ ወገኖቼ ሲሰጠኙ የበለጠ ሐሴት አገኘሁበት። አዎና! እኔ እኮ ስጽፍ በውስጤ ሁኜ ነው። የፓርቲ አባል ዬማልሆነውም ለዚህ ነው። በዲስፕሊን መታሰር አልሻም። ፓርቲዬንም ማስነቀስ አልፈልግም። እንዲህ በልቅ ዓለም መኖር፤ በምንም ነገር ያላታሰረ ነፃነት እሻለሁ። ባሩዱ ተነጣጠረ ዓላማውን ሳይስት ጦሮዎ በጠላት ሰፈር ልኮ እንዲህ ቆርቆሮውን ቢና ጢናውን አወጣው። ዓይነተኛ የውስጥ ተቆርቋሪ ይሄው እንዲህ  ከእንቅልፍ ጋር ተጣልቶ ጎልቶ አውሎ ያሳድራል ጌታውን ሲያስጨር። ተመስገን – አነቃነቀ – ናጠም።

በግራ ቀኝ ስውርና ረቂቅ ሴራ በጠላት እጅ ለወደቀ – ስለ ራሱ ቆሞ ሊናገር ለማይችል፤ በጠላት እጅ በመንፈስ ማደንዘዣ የበቀል መርዝ ሙከራ የሚሠራበት ታላቅ ወገኔ በሌለበት ቦታ ስለ እሱ ተናግሬ ወንጀለኛ መሆን ክብር ነው – ለሥርጉትዬ። ይልቅ ያልተገባኝን ክብር ባልተገባኝ ወቅት ሰጡኝና ከነፃነት አባት ጋር አንጠለጠሉኝ። ከአንድ የነፃነት ሙሴ – ሰማዕት ጋር ደረጃዬ አይፈቅድም። ይህ ባይሆን ጥሩ ነበር። ይሄ ወቅትን ጊዜን ያልጠበቀ ከፍ ማለት አልወደወም። አጉል መንጠራራትን ፈጥሮ እሸት ቅመሱ ሳይባል ዘጭ ያደርጋልና። ለዚህም ነው በብዕር ሥሜ እምጽፈው። እንጂ እኔ እህታችሁ በተፈጥሮዬ ደስታ ላይ አልገኝም። ከተሸነፈ ወይንም ከተጠቃ ጋር ግን ማን ይዞኝ። ባለፈው ዓመት የተከበሩ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ እዚህ መጥተው አባላቱን ካነጋገሩ በኋላ እንዲሁም በተለዬ ሁኔታ ለሚያግዙ የነፃነት ትግሉን ግንባር ቀደም „አክቲቢስቶች“ ነው የሚባለው ከእነሱ ጋር እንደተወያዩም አዳምጬ ነበር። አሁን ደግሞ ፎቶም አይቻለሁ። ለእኔ ይህ ጉዳዬ አይደለም። ድንበር አለው ኑሮዬም – ተፈጥሮዬም።

አንድ ነገር – እንዲህ ሆነላችሁ ክብርት ዳኛ ብርቱካን ሜዴቅሳ ታስራ በነበረች ወቅት በዬሳምነቱ እደውል ነበር ለቤተሰብ። እምችለውን የመንፈስ ደጋፍ አድርጌያለሁ ብዬ አስባለሁ። ስትፈታ ግን አልደወልኩም። ኢሜሏም አድራሻውም አላስፈለገኝም። አላገኘኋትም።

ለእኔ ቁም ነገሩ ጠላት እንዲህ ጥቃት ሲፈጽም፤ ሰብዕዊነትን ሲዳፈር፤ የዜግነት መንፈስ ሲጨፈለቅ፤ ህግ በጠራራ ፀሐይ በጉልበተኛው ወያኔ ሲረሸን የእኔ ብዬ መቀበል – በግንባር በባለቤትን በዕውነታዊ ውስጥ መገኘት ነው። እንዲያውም ጀግናዬ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ የግል ህይወታቸውን ከተከበሩ ወንድማቸው ከሰማሁ በኋላ የበለጠ ነው እኔን ዬመረመረኝ። እንዲህ በአደገ ሀገር በአንዲት ክፍል ቤት ሁሉንም ዓይነት አማራጭ ደፍሮ ለመሞከር እራስን ረስቶ ታጥቆ መጠበቅ ልዩ ጸጋ ነው። መታደል – የእውነት። እና  መከራን ለፈቀደ ወገን መሰከራችሁ ነው „ናዚነቱ ሆነ ጉዲትነቱ“። ወቅትንና ጊዜን ማድመጥ በሚመለከት ለሽበት መንገር ወንዝን አሻቅበህ ተጓዝ እንደማለት ከቶ ይሆንብኝን? ግድፈቱ ዘመን ይቅር አይለውም – ጌታው። ግራጫ አለቀሰ – እዬተቀነሰ – እዬተበጠሰ …. ከቶ ይህቺ ስንኝ ተመቼዎትን?!

ሌላው ከትክት ብዬ በፈንጠርጣራ ጥርሶቼ የሳቅኩት ደግሞ በነፃነት ሀገር ፈቃድ ጥዬቃ መዝመት ነበረብን ወደ ዘመን ሰጡ ጌታው። ወይ አቅምን አለማወቅ?! „ልክን ማወቅ ከልክ ያደርሳል“ ይላል ጎንደሬ ሲተርት።  ሃሳብን በሃሳብ መታገል የአባት። ድንበር ዘለል የጎጥ አገዛዝ ለዛውም ነጭ ሀገር ግን እማይቻል ልግጫ ነው። ዝለት – በፍዘት ይሉታል ዕብኑን ህልም። ለነገሩ የጎጥ በሽታ ከዚህ በላይ መሄድ አይችልም … በጣም ረጅም ጊዜ እኮ ነው፤ 23 ዓመት መስሎ – ተመሳስሎ መኖር መርግ ነው አቅልን የሚፈትል።

መኖር ማለት መኖር የለገሰውን ተፈጥሯዊ ጸጋና ክህሎት በጊዜ አውቆ ተጠቃሚ መሆን መቻል ነው። መቻል ደግሞ እራስን ሆኖ እንደ ራስ ሆኖ በመጤ እንደራሴ ሳይጠቀለሉ እንዲህ አደባባይ ላይ ወጥቶ ውስጥን ማስጎብኘት ነው። ይህ መሸቢያ መንገድ ነው። ስለምን? ድርጀቶችን ተጠልሎ ጥቃት መፈጸም ሆነ ወቅትን አስታኮ ማመስ ከምድር በታች ይቀበራሉና። ብዙ ድርጅቶች ታሪካዊ ስህተት የሚፈጽሙት በእንዲህ ዓይነት ዝበትና ግብዝነት በጎበኛቸው መንፈሶች የዋህ ወገኖች በቅንነትና በአዎንታዊ ተመልክተው ይጥቅማል በማለት ሃሳብን ስለሚያስተናግዱ ነው። ስንሰበሰብ ሲበተን፤ አፍሰን ስንለቅም ወይንም ለቅመን ስናፈስ የኖርነው … በዚህ ጆሮ አልቦሽ መንገድ ነበር።

ከእንግዲህ ያ ይናፈቅ የነበረ ዬናሙናዊነት መለዮ ልዑቅ ክብር፤ ተወዶና ተፈቅዶ የተለገሰው ንጡር ፍቅር፤ በብዙኃኑ የተጫነለወት ልዩ ዘውድ ተምልሶ ዳግም አይገኝም። ቁርጠዎትን ይወቁ – ጌታው። ዬትኛው ጌታቸው ረዳ? የኛው ወይንስ የወያኔው? ….. መለያወት ላቂያ ፍቅር ነበረው። ጌጥማ አቅርቦትና ልዩ ዜማዊ አክብሮት – ቅርበትም በነኑ – ስለፈቀዱላቸው። የአብነት ት/ቤት – ነትወትንም ለዘለዓለም ከረቸሙት – ምነው እንዲህ – የጤና?! ከብዙኃኑ ቤተኝነት መውጣትስ ይመች ይሆን? ይህ ግንፍል ግንፍል ማለቱስ — ?

ማንም ሰው እንደ ሰው በምድር ላይ ብዙ ነገር ሊኖረው ይችላል። ከሁሉ የሚልቀው ግን የህዝብ ፍቅር ሃብት ነው። ፍቅር የተጠረገ ልብና ብቁ አስተዳዳሪን ይሻል። ፍቅር አድማጭና ተናጋሪም ነው። ስለፍቅር መሸነፍም ውስጥን እንደ ተፈጥሮው እንዲኖር መፍቀድ ነው። ይህን ሁሉ ዘመን በነፃነት የኖረ አባወራ በመዳፉ ላይ ያለውን የህዝብን ፍቅርን በአግባቡ ለማስተዳደር አቅቶት ወይንም ግራጫዊ ዘመን ዘለቅ ተመከሮው መተርጎም ተስኖት እንዲህ እናት ሀገር ማቅ ለብሳ በማህጸኗ የደም ዕንባ በምታለቅስበት እጅግ በጠቆረ ዘመኗ፤ በከፋት ዘመኗ፤ ሾልኮ መቅረት ….. ብልሃት የሌለው ቅላት ነው ለእኔ።

እኔ ሰው ነኝ። ከዚህ በላይ ስለ እኔ የሚተረጉም ምንም አልፈልግም። እርስዎ ግን አስፈለገዎት። በአደገው ሀገር ተቀመጠው ዘመን የሰጠውን፤ የፈቀደውን ፍትህና ነፃነት አግኝተው እዬኖሩ በጣም ታች ወረዱ። ጎሳ ላይ -

ዘመነዎትና ተመክሮዎት ውስጥዎትን ለማሸነፍ አቅልም  - አቅም አነሰው። ምነው ቸኮሉ?! ኩታረነቱን* ለልጅ መስጠት ይገባ ነበር። ምን ቆጠቆጠዎት? ምን እንዲህ አንተከተከዎት? ምን አበሳጨዎት? ምን አቅለዎትን ነስቶ በነፈሰበት መረጃ አካልዎትን የገዛ ቤተሰቦወትን ለመወንጀል ምን አስነሳዎት? የምን ጥድፊያ ነው ትቅማጥ እንደያዘው ሰው?

እኔ ልመልሰው። እስከ ዛሬ ድርስ እራስዎትን አሸንፈው አልኖሩም ነበር። ፍላጎቶዎትና እርስዎ አብራችሁ አልነበራችሁም። ወይንም ውስጥወትን አያውቁትም ነበር። ከዚህ የከፋ ነገርም እኮ ሊመጣ ይችላል። በደለኛ እስካለ ድረስ። ሰው እራሱን ሳያውቅ ወይንም እራሱን ሳያዳምጥ ሲኖር አንድ ቀን እንዲህ እራሱን ፈልጎ ያገኛዋል። እሱን ያገኘው ዕለት እንዲህ ይቧርቃል። ሜዳውም ሸንተረሩም አይበቁትም። ይጠበዋል። ታፍኖ እንደ ኖረ ስለሚቆጥረውም ይተነፍሰውና እንዲህ ይወጣለታል። እንኳን ለዚህ አበቃዎት – ጌታው። እንጡሩብ አዘለለዎት …. ነዘረዎት – ሰረሰረዎት።

መመካት ቢኖር አብነት ላለው – ትንሽ ብጣቂ የመንፈስ ማረፊያ ዬብትን አፈር ተቆርቋሪነት ቢኖር ነበር። አንድ የመንደር ወመኔ ስብስብ የፈጸመው ኢትዮጵያ ኢትዮጵያ የሚል ጣዕም ቢኖረው፤ ወይንም ሰውኛ ያለው ጠረኑ ቋት የሚሞላ ተግባር ላይ የሚታይ ተጨባጭ ነገር ቢኖር በነበር። ዕድሉን ቢጠቀምበት በነበረ። ጭብጦ አኮ የለም።  የፈለሰ = የመከነ – የተፋቀ፤ የፈሰሰበት ዘመን ጥልማሞተ ነው የወያኔ ያረገዘው ዘመኑ። ምን ተነስቶ ምንስ ተጥሎ? …. በወያኔ ያልተበከለ ወይንም ያልተጠቃ – ያልተቃጠለ ተቋም ምን አለና? መርዝ!

ጸሐፊ ጌታቸው እረዳ እንደ እርስዎ ያለ ታላቅ የዕድሜም ባለጸጋ፤ በፖለቲካ ልምድ የበለጸገ አባወራ፤ በቀለም ትምህርትም ሙሑርነቱ ታክሎበት „ከትግራይ የወጣ፤ ከትግራይ የተፈለፈለ እጭ’፤ ትግራይን ነፃ እናወጣለን ብለው የተነሱ ጎጠኞች፤ ሀገርና ትውልድን የገደሉ፤ ትውፊትና ማንነትን የቀበሩ፤ የሀገራችን አካል የጎረዱ፤ ዜግነታችን የጠቀጠቁ፤ በዘር እዬነጠሉ ያጠቁ፤ እረቂቅ ዛሬ የማናያቸው ነገ ግን እዬፈነዱ ሀገር አልባ የሚያደርጉን ደባ የፈጸሙ፤ ሰንድቅዓላማን የተዳፈሩ – የተጸዬፉም፤ ባህልን ካለርህራሄ የጠቀጠቁ፤ ግብረ ሰዶምን ያበረታቱ፤ የዕምነት ምኩራቦችን በትዕቢት የረገጡ፤ በወገኖቻችን ላይ አራዊታዊ ተግባር የሚፈጽሙ፤ ሀገራቸውን በጠላትነት ፈርጀው ተቋማቷን ሁሉ ያከሰሉ፤ ጥርጣሬን ያነገሡ፤ ምቀኝነትን ያፋፉ፤ አብሮነትን በተባይ ያስወረሩ….“ ምኑ ያልቃል እንዲህ አውሎ ጎልቶ በሚያሳደር የብዕር እልልታ ጎሽ ያሰኝ ነበርን? ህሊና ቢኖርስ አንገት ያስደፋል። ያሳፍራል?

ብዕረኛው ቢያውቁትና ቢገነዘቡት ዛሬ ወያኔ በሚፈጽመው በደል የተፈጠረበት መሬት ያለው ንክኪ ሁሉ ቁስል ነው። መግልን ፈቅዶ ያዘለ። አጋጣሚው ቢሾልክ እንዴት እልቂትን በቀለን ታግሶ ምህረት ማውረድ እንደሚቻል በዚህ መስመር ነበር ምርምር ሊያደርጉበት የሚገባ። እኛ አንቅልፍ የነሳን ይህ ነው። …. ጀግና አንዳርጋቸው ጽጌን የማድንቅበት ትልቁ መስፈርቴ ይህን የተፈራ አምክንዮ ሁሉን ችለው – ዘለፋውን ሁሉ ተሸክመው፤ ወጨፈውን ሁሉ ተቋቁመው ደፈረው መግባታቸው ነው። ጤናማ የመተንፈሻ ቧንቧ ለመዘርጋት አብነቱ ነበሩ – ቀንዲል

እንደ እርስዎ ያለ በልምድና በተመክሮ ከለማ ወገን እምንጠብቀው የነበረ የበቀል ተጠቂ ተቋማትና ወገን ለማዳን የትግራይን ዬኢትዮጵያዊነት ጉልተኝነት ለማስከበር ፊተኛው ረድፍ ላይ ቆመው እሳቱን ቋያውን እንዲቀበሉ ነበር። ተዉ! በቃ! በዛ! እንዲሉ ነበር። እንጂ እንዲህ አይጥ የበላው ጨርቅ የመሰለ ብትክትክ ያለ፤ በዬቦታው የተቦጫጨቀ፤ ዘሎ ፈርጦ ዪሚወራጭ የነገር ጅምናስቲክ አስተሳሰብ ይዘው ብዕርና ብራናን ሲያገናኙ አንገትን ቀና አድርጎ ለመሄድ  ከእንግዲህ ጋዳ ነው የሚሆነው። ፍሰኃና ሰናይ ከሆነወት —— ስ

እውነቱን ብነግረዎት ለትግራይና ለትግራይ ህዝብም የእርስዎ መስመር መዳህኒቱ አይሆንም። በፍጹም። …. ደግሞስ ወጪውንስ ጉዞውንስ እንዴት ቻሉት? – የቀረዎት ሀገር፤ የቀረዎት ሰው፤ የቀረዎት የነፃነት መንፈስ የለም። አዳረሱት። ግን ብዕሮዎት እንዲህ ዟሪ ናት? … ኧረ እንዲህ ስድ አደግማ አያድረጓት!…. የጠብ ተጠማኝም አያድርጓት። እ! መንጠራራቷም ልክ ቢኖረው መልካም ነው። ምን አልባት እርስዎን እረስታ በራሷ ኢጎ መጪ ብላ ይሆን? ኧረ በፈጠረዎ ልጓም ቢጤ ይፈልጉላት …. እዘጭ ያደረገችው እኮ ትልቁን ዳቦ …. እም! አቤት ያንት ያለህ! ከስንቱ ረገጠች? ደግሞ ጠላት ማብዛት ግጥሟ ሆኖ አረፈ — አፈርም ላይ ፈርፈር አለች …. ተጋግጣ – ህም!

አሁን ባለው ሁኔታ የወያኔ ሃርነት ትግራይ ጎሽ እንኳንም የኛ ሆናችሁ የሚያስብልበት ጊዜ አይደለም። የትግራይን ክብርና ዝና የፈገፈገ የጎጥ ስብስብ ከረፋህን ብሎ ትግራይን ማዳን ማለት ለእኔ ኢትዮጵያን ማዳን ስለሆነ፤ በዚህ በጣም የተጋ ተግባር በተከታታይነት በተከወነበት ነበር። መሬት ያያዘ፤ ጭብጥን የተንተራሰ፤ ሥልጡን – እርጋታ የከበከበው የምርምር ድርጊት ያስፈልግ ነበር። የማዳን ዘመቻ እራስን አቅልጦ …..

የብዕረዎት ጠብታ ግን ጦርነት ነው ያወጀች ….. ይገባልን? በመገዳደል፤ በመጨፋጨፍ፤ በጥላቻ በተከዘነ ጎጣዊ ጉዞ ሀገርና ህዝብ ይድናሉን? ለመሆኑ ሽበተዎት በውስጥ ወይንስ ውጪ ላይ ነው ያለው ይሆን? ለሰው አይደለም ለታሪክ – ለትውፊት – ለሀገር – ለሰንድቅአላማ – ለአደራ -ሽምግልና በሚያስፈልጉበት ጊዜ እንዲህ ያለ መላቅጡ የጠፋ የጎረና ጉርና ነዳላ አስተሳሰብ ይዞ መቅረብ ከቶ ወደ ዬትኛው ዕድሜዎት ላይ ተመልሰው ይሆን?

አሁንም አልጠገቡም ይጽፋሉ። ስህተቶችን አነባብረው እዬካቡ ነው። ቃላቶቹ አምጸው – ተንደው ቢደርምሰዎትስ? ሞትንም እርሰዎም ብዕረዎት እረሱ መሰል። ሰው ያዘነበትም ሰው ….. የበቀል አምላክ አለና ይበቀላል። „ላም ባልዋለበት ኩበት ለቀማ“ አድርገው ጭንግፍ ያደረጓችን የነገ ወጣቶች እኛ ህይወቱ ባይኖረን ወላጆቻቸው ያነባሉ — ሀገርም ….. ታነባላች። ጊዜያቸውን – ጉልበታቸውን – ገንዘባቸውን – እያፈሰሱ፤ ደፍረው ቅራኔ ውስጥ እዬገቡ፤ ሌትና ቀን በሚተጉ የነፃነት አርበኞች፤ ወጣትነታቸው ሳያውቁት አልፎ ሲሄድ እያዬዩት ኑሮን ንቀው ነገን በተግባር በሚያደምቁት ላይ …. እነዚህ ፎቷቸውን በማናለብኝነት የለጠፏቸው ወጣቶች አንድ ነገር በህይወታቸው ቢደርስ – ተጠያቂ መሆነዎትን ግን ልብ ብለውታልን? …. ከልበዎት ሆነው ይስቡት። ጹሑፎዎትንም ደግሞው ያንብቡት። ተኝተውም ይሰቡ። ግን ግን እርሰዎ ነው የጻፉት ወይንስ ኮበሌው ጌታቸው ይሆን የጻፈለዎት …..? አምላኬ! ተሳህለነ!

„ኢትዮጵያዊነትን ሃይማኖታቸው“ ስላደረጉ ብቻ ፎቷቸውን የለጠፉት ወጣቶች ወያኔ አፍኖ ወስዶ ምን እንዲያደርጋቸው ይሆን የፈለጉት? ወይንም ሽፍታው ወያኔ የሞት ቅጣት ወይንም ዕድሜ ልክ እስራት ፈርዶባቸው በዛ ተደናግጠው ምን እንዲሆኑ ይሆን ምኞተዎትና ዓላማዎት? ወይንም አንዱ እንዲህ እራሱ የሾለከበት የዘር በሽተኛ  ባገኘው አጋጣሚ  አነጣጥሮ እንዲገድላቸው ይሆን? ለምንስ መሳሪያውን ገዝተው አይሰጡትም ለአንዱ የዘር ብኩን?! ….. ገድለዋቸዋል እኮ እርስዎ። ሞት እኮ ነው የፈረዱባቸው።

እኔ እኮ እበቃዎት ነበር – ጌታው። የጻፍኩት እኔ። ስለምንድነው ሳቢያ ዬሚፈልጉት። „አንዳርጋቸው ስለምን ጀግና ተባለ?“ ነው አይደል። ጸሐፊዋ እኮ እኔ ሥርጉተ ሥላሴ ነኝ። ፎቶዬ ከናፈቀዎት ከፈለጉት ላይ ይለብዱት። በፈሉጉት ዘይቤ ይሰልቁኝ። እንዳሻዎ ይቀጥቅጡኝ። እኔ እመመኘው ነፃነት የማይመቸኘን ሃሳብ ለማስመቸት ነው። ሃሳብን በሃሳብና በፋክት አፋጭቶ በነጠረው ሃሳብ በብዙሃን ድምጽ የሚመራ ነፃነት ነው ናፍቆቴ። ስለሆነም በፈለጉት ዓይነት አቀራረብ ዱላዎት ይደላው ነበር። እችለዋለሁ። ምንም እንኳን ጹሑፎ ብናኝ ጭብጥ ባይኖረውም – እንኩቶ ቢሆንም።

ከእነዚህ ወጣቶች እራስ ግን መውረድ አለበዎት። ፎቷቸውንም ማንሳት። ትእዛዝ አይደለም – አስተያዬት እንጂ። እኔና እርስዎ አንደራረስም እርስዎ ከፍ ያሉ እኔ ደግሞ ትቢያ። በሁሉም ነገር እንደሚበልጡኝ አሳምሬ አውቃለሁ። ለዚህም ነበር በጭምትነት ዝም ብዬ የሰነበትኩት። እርስዎ ግን የከተቡት ሁሉ የተሰባባረ – አቅጣጫው የጠፋበት – የወለላለቀ – ወለምታው የሰቀዘው የቃላት ድርደር ሁሉ ቁጭተዎትን፤ ለወያኔ ያለዎትን መጠነ ሰፊ ተቆርቋሪነተዎትን ሁሉ ሊመክትለውት አልቻለም። መደረት – መደረት በላይ በላይ – ከሽበተዎት ጋር ይምከሩ።

እኔ ልንገርዎት ዓላማው የሥነ – ልቦና ጦርነት በውጪ የነፃነት ታጋይ ቤተሰብ ለመሰንዘር ነው። ችግሩ አንተዋወቅም። ከብረት ቁርጥራጭ ዬተሰራው መንፈሳችን ግን ከቶውንም ለአፍታ አያንቀላፋም። ጠላታችን ወያኔ ፋሽስታዊ ማኒፌስቶው እስኪነቀል ድረስ የነፃነት ትግሉ በበቃን መሪነት ይቀጥላል። ለሰማዕትነት የቆረጠ ጀግና በጠላት እጅ ነው። ውስጡን ጎርጉራችሁ ምን እንዳደረጋችሁት አይተናል። ይህ ደግሞ ሃይልና አቅም እንደ አዲስ እዬፋፋ እንዲሄድ ያደርገዋል። አንፈራም! አንገታታችንም አንደፋም – በፍጹም።

በስሜት ጋልበንም ከህዝብ ፍቅር ማሳ አንወጣም። ይህ ይመረወታል – ይወረወታልም። ይህ ተቆስቁሶ „ትግራይን“ እንደናብጠለጥል ነበር የፈለጉት። ጓደኛ ፍለጋም እዬባዘኑ ነው። በዓይናችን በተከበሩ አቶ ገ/ድህን አርያማ አይምጡ። አዩ ቅናት! እኔ ስነግረዎት –  የተጠለሉበት ጥግ ቀን ዋቢ የለውም። ቀን ወዳጅ የለውም – አውላላ ሜዳ ላይ ጥሎዎት እንዲህ እብስ -

የፈሩት – እንዲህ ያባከነዎት የተከበሩ የአቶ አንዳርጋቸው ዝክረ ጀግንነት በቋሚነት ጽላታችን ይሆናል – ለአብዛኞቻችን። ተከፍሎን ወይንም ባውንድ ተሸልመን አይደለም። እንዲያውም እንዲህ አቅም ሆነን ማገር እንዳንሆን የራሳችን ቅንቅኖችን እዬተጋፋን – እዬገፈተርን ነው ዕውነትና ሃቅን ለማድመጥ የፈቀድነው። በገንዘብ ተገዝቶ ዕንባና ጥቁር ልብስ ሄሮድስ መለስን ቀበረ። እኛ ግን  ለአርበኞቻችን – ለሰማዕቶቻችን ፈቅደንና ወደን ደስ ብሎን የምናደርገው ድርጊት ነው …. ለህሊና መኖር ማለት ተፈጥሮን የመተርጎም አቅምና ብቃት ማለት ነው።

መላሾ አሞሌ እኔ ሳውቀው ለከብት እንጂ ለሰው ልጅ አይታሰብም።  የወያኔ ሥር ለማረግረግ ጥሎሹ ወይንም እጅ መንሻው እንደልቡሻ ማይጨውና መተማን እንዲሁም ሌሎች ሀገር ወዳድ ወገኖቼን ታሪካቸውን አቃጥለው፤ ሞት ፈርደው ሲባትሉ ሰነበቱ። መጥኔ ለእርስዎና ለአውቆ አበድ ብዕርዎ። እኔ ልንገረዎ እንደ እግር እሳት ያንገበገበዎት ለወያኔ ሽፋን ለመስጠት በሰላማዊ ትግሉ ስም ጠንከር ብለው የሚወጡትን የነፃነት ድርጅቶችን በውስጥ ለውስጥ መንገድ ስትንዱ፤ ስታናክሱ፤ አንጃ ስታስፈጥሩ በዚህ ለሰው በማይታይ ደባ እሳካሁን አረሙ ወያኔ ትንፋሹን እዬሰበሰባ የተፈጠረበትን የጥፋትና የባንዳነት ተልዕኮውን ሲከውን ኖረ።

ከዛም በፊት አልተሳካም እንጂ ኢትዮጵያና ኢትዮጵያዊነትን በሚያመክኑ ሥውር ሴራ ረቂቅ በሆነ – ሰልጠን ባለ መንገድ ፍርሻ -ህውክት – ሲፈጠር ማገዶዎች ሌሎች ነበሩ። አሁን ጥግ ጠፋ …. በጠራራ ጸሐይ መሸፈኛ አልባ  ገመና መውጣቱ ግድ ሆነ። የወገን የበዛ ሰቃይ የምትፈሩትን አቅም በመንፈስ ጽዑም ለዛ አጋባና ፋሽስቱን ወያኔ ፊት ለፊት ወጥቶ አወገዘ። ይህ ሲቀጠል ደግሞ ተከታዩ ምን ሊሆን እንደሚችል ታውቁታላችሁ …. አጃቢ ጠፋ … አቆላማጭ ጠፋ …. ሸፋኝ ጠፋ …. ቅኖች ዛሬን አነበቡ ….. ሚስጥር ተግልጦ እንዲህ በጉባኤ ሥጋና ደምን አዋህደ፤ የሀገራችን ውርዴት ውርዴታችን ነው አሉ ዬእትብት የቁርጥ ቀን አላማና ራዕይ ያላቸው ልጆቿ እንሆ ፊት ላይ ተገኙ። የወገናችን ስቃዩ ስቃያችን ነው አሉ የትውፊት አንበሶች።  የወገናችን መከራው መከራችን ብለው ሆ! ብለው እንደ ትሩፋታቸው ተነሱ። ሌሎችም በዚህ በመከራ ቀን መታቀብ አለብን ብለው ሰብሰብ ብለው ተቀመጡ። ወቀሳ የለ ነቀሳ የለ። መነገድ በቃ ….. እዬተጣቡ መጣባት ማብቃት አለበት አሉ። ወሰኑ  - ቆረጡ – ተንቀሳቀሱ። ይህ ደግሞ መሽጎ ብቅ እያለ ቤንዚን ለሚያርከፈክፈው አልማጭ አልተመቸም።

ጭድ ከማቀበሉ በፊት ሃሳቡና እልሙ ጭድ ሆኖ አረፈ። ራሱን ገልብጦ አቃጠለው። እኔ እንደማስበው ወቅቱን በአግባቡ አድምጦ ማስተዳደር ከተቻለ አሁን የነፃነት ትግሉ ከጠራ መስመር ላይ ይገኛል። በእጣት የምትቆጠሩ ወገኖች በሰላማዊ ትግል ሥም፤ ወይንም በሉዕላዊነት ተቆርቋሪነት ሥም፤ ወይንም ሊዋህዱ ባልቻሉ የአንድነቱ ቤተሰቦች ሥም ወይንም በሃይማኖት ሥም፤ ወይንም በብሄርና ብሄረሰቦች ሥም ስሱን ቦታ እያዩ ካቫውን ደረብ አድርጎ ጠቅ እያደረጉ አጋግሞ ዞር፤ ወይንም እኔም አለሁ እያሉ እዬገቡ ማመስና ማተራመስ አይቻልም። ቀኑ እንደ ክብረዎት ሾለከ …. አዬ ቀን! …. እርግጥ ሲያስቡት ጎሽ መሸቢያ የሚባሉ መስሎዎት ነበር። በጣም ብዙ ሰው ነው ያዘነቦዎት።

እጅግ የምትናፍቁኝ የሀገሬ ልጆች በዚህ ዓመት ብቻ ሁለት ነገር ተከሰተ። ጀግና ካፒቴን አበራ ሃይለመድህን በሚመለከት በተፈጠሩ ክስተቶች በዬቦታው እጅግ በጣም ብዙ ነገር ነው የተዝረከረከው፤ የነፃነት ትግሉ አካል ተብለው ባለወርቅ ተክሊል ባለቤት የነበሩትን ሁሉ ነው የዛ ጀግና ድል ያንዘረዘረው – ካልጎሽ አይጣራ፤

ከዚህ ቀጥሎ ጀግናዬ አንዳርጋቸው ጽጌን በማፍያ ትብብር ከወያኔ እጅ መግባት በሚመለከት ደማችን የተቆጣ ሃይሎች የሀገራችን ክብር መደፈር ያነገበገበን ወገኖች፤ በገፍ ሰላማዊ ቀንበጥ አርበኞቻችን ወደ እስር እዬተጣሉ በሚወሰድባቸው ፋሽስታዊ ህገ ወጥ እርምጃ ይግርመዎታል ብዕረኛው አቶ ጌታቸው እረዳ ጉዳያችን ነው ብለን አካላችን እንዳይመስለዎት መንፈሳችን በፈቃድ አጋባን። በቃ! ተሰደንም ሰላም እንዴት እናጣለን ብለን ለይ አልን። ….. ለስላሳዊ ተፈጥሯዊ ባህሪያችን ጎርበጥባጣ ሆነ … ልንመች አልቻልነም። እኔ እንዲያውም ቆርጫለሁ የፈለገ ህዝባዊ ስበሰባ ይሁን አቋሙ ባለዬ፤ በተወዛወዘ ቦታ አልገኝም። ብዕሬም ብራናዬም መደከም የለባትም። በሃይማኖት፤ በማህበራዊ ግንኙነት ሁሉ ጥርት ባለ መስመር መድከም – ለትርፍ፤ በስተቀር ለኪሳራ ቆራጣ ነገር አይባክንም ከእንግዲህ።

ኢትዮጵያዊነት ሃይማኖታችን፤ ኢትዮጵያዊነት ቀለበታችን፤ ኢትዮጵያዊነት ድምጻችን፤ ኢትዮጵያዊነት ቀለማችን፤ ኢትዮጵያዊነት ህገ – መንግሥታችን፤  ኢትዮጵያዊነት ቅኔያችን፤ ኢትዮጵያዊነት ውስጣችን ብለን እነሆ ተነሳን። የሃይላችን ምንጩ – የሃይላችን ጭንቅላቱ – የሃይላችን ጉልበቱ – ብንዘገይም እግዚአብሄር ምክንያት ሰጥቶ ከቀስት እናመልጥበት ዘንድ አጥቢያ ኮከብ አበራልን።

ይህ ነው ፋታ ነስቶ – እረፍት ነስቶ አምክንዮው የፈለሰበት፤ ጠረኑ የተበተነ፤ መግቢያና መውጫው የተተበተበ፤ ፍላጎቱ እንጡሩብ የሚዘል፣ አንድም መረጃ ሊቀርብበት ያልቻለ ብትክ – ብትክትክ ያለ የቃላት ድርድር ያሰነበቡን።  …. ድጋሚ እንኳን ደስ አለዎት እራስዎትን ስላገኙ። ከመሼ ቢሆንም። ከቻሉ በመጪው ምርጫ ለጠ/ሚር ውድር ወይንም ለከዘራ ደጋፊነት ይወዳደሩ …. ምን ሻታ ያዞረዎታል? … ከዘራ ስል እርጅና ማለቴ አይደለም። አልወጣኝም እንዲያውም ብዕረዎት በሬ ወለደ ናት እንኳንስ እኔ ብዬ። ለማለት የፈለግኩት ስንት ናቸው የሽፍታው ዬወያኔ ም/ጠ ሚር …. ለነገሩ በመጪው ምርጫ ያው ዘሬን ዘሬን እያለ የሚዳጭረው አቶ ወንበር  ከቦታው ወርቃማውን ካገኘ ከዘራ ላያስፈልገው ይችል ይሆናል …. ከዛ በፊት ግን ነፍሳችን በመቋጠሪያ አልያዝናትም ሁላችንም …. ማን ያውቃል የሁለት ቢላዋ ባላቤቶች …. ሽኝት ቢጤ ይኖር ይሆን? ወፏን ጥያቄ መሄድ ….. አሰኘኝ …. እንደ ማለት —-

ሌላው እንዲያውቁት ዬምፈልገው ነገር ኢትዮጵዊ ተቋማቱ የመወያያ መድረኮች ስለምን እንዲህ „የናዚ ኔት ወርክ“ እስከማለት አደረስዎት ቢባል። ለዘር – ለመንደር በሽተኞች „ኢትዮጵያ“ የምትል ሥም ሁሉ ዛር ታስወርዳላች …. የወያኔ ተልዕኮ ይህቺን ምድር በተፈለገው መልክ ማጥፋት ነው። ይመኟት የነበሩት ባእድ ሀገሮችም እነሱ ስላልቻሉ ከማህጸኗ በፈሉ ተውሳኮች ፍላጎታቸውን በማስፈጸም ላይ ይገኛሉ።….ሽፍታው ወ ያኔ መሰረተ ጥንስሱ በአንድ ዘር የበላይነት ኢትዮጵያዊነትን ለማጠፋት፤ ለመደምሰስ በተከታታይነተትና በትጋት መሥራቱ ፍጥረተ ነገሩ ነው። ሲከስም ግን ከሥሩ ዘር አልባ ሆኖ ይሆናል። እኔ እምሻው እንደዚህ ነው  …  መርዝ መነቀል አለበት።!

ሌላው ቀርቶ ወያኔን የተገባውን ያህል „ለትግራይ“ አላደረገም ወይንም በደሉ መረን ለቀቀ እቃወመዋለሁ ብሎ የሚነሳ አንድም ድርጅት ወይንም አንድም የመወያያ ክፍል „ኢትዮጵያ“ የምትለውን አስቀድሞ አያውቅም። አይደፍሯትም። ቀዳሚው …. ለምን ይህ አልጎረበጠወትም? ይመቸወት ይሆን  - የሸረፋ ሸጎሬ?

አቶ ጌታቸው ረዳ ጹሑፎዎት በጣም ቁንጥንጥ ያበዛ ቁንጣን ያያዘው ነበር። እጅግ አብዝቶ የዕድሜዎትን ተፈጥሯዊ ጸጋ ሁሉ ድጦታል ልበልን? ጥንቃቄ ፈጽሞ አልጎበኘውም። ማገናዘቢያው ሆነ ማመሳካሪያው የእንቧይ ካብ ነበር። እንዲህ የሚጋልብ ስሜታዊነት ኢትዮጵያንም ሆነ ኢትዮጵያዊነትን አያድንም። የሳሙና አረፋ ያውቃሉ? ወይንም  ፈረሰኛ ውሃ ሙላት የሚባል እንደዛ ነው ልበልን? ኢትዮጵያና ኢትዮጵያዊነትን የሚያድነው ከበቀል የጸዳ ከቂም የነፃ እራስን በፍጹም ሁኔታ ያሸነፈ፤ ውስጥን በሚገባ መቆጣጠር የቻለ፤ ዬባህላዊ ትውፊታችን ህግጋት በስክነት ያወያዬ መንገድ ብቻ ኢትዮጵያን እንደ ሀገር ኢትዮጵያዊነት እንደማንነት መግለጫ ያድነዋል። በዚህ ሃዲድ ብቻ ትውልዱ ከአፍር ለማኝነት ይድናል። በስተቀር ግን ዛሬ ስንዴ ነገ ደግሞ ከበለጸጉ ሀገሮች አፈር ለማኝ መሆናችን አይቀሬ ነው። የአንድነቱ ዋቢ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ በወያኔ አቅም ብቻ አይደለም ለዚህ የበቁት። ዬኢትዮጵያ ዬአፍሪካ ቀንድነት፤ የመካከለኛው አፍሪካ እራስነት መናድ በጥረታቸው የማይቻል መሆኑን ሲያውቁ ከውስጧ ባንዳ አመረቱላት። ይህ ዕውን እንዳይሆን ነው የሴራው ድርና ማግ። ለማንኛውም በዚህ ሳይሞቅ እንደ ጉድ በሚፈላ ኮበሌ ብዕርና ብራና የተበዳይን – የመከራን – የግፉዕንን ሰዉ ትእግስቱን ያሸፍታል። አይገባም። እልህና ቁጭት ሌላም እሳት ያቀጣላል። የከረፋ በደል አለ። የሚያንገሸግሽ አድሎ አለ። የሚያንገፈግፍ መገፋት አለ።

በከረፋው በደል ውስጥ ወያኔ እንዲሸፈን ሽፋን ፈልጎ የትግራይን ህዝብ ምሽጉ አድርጓል። ይህን ሚስጥር ተፈልፍሎ እንዲገኝ ማስተዋል ተንበርክኮ ይጠይቃል። ማስተዋል ሱባኤ ላይ ነው። ዕንባም ህማማት ላይ። ስለሆነም መርዛማ እጩን ለይቶ ነቅሎ ዬማውጣት ሥራ ነው መሠራት ያለበት። እርስዎ እያሉን ያሉት ደግሞ ሌላ በበቀል የጨቀዬ – ጨቀጨቅ ከሃሞት ጋር አንድንጎርስ ነው። ቢያዳምጡኝ ምልዕትን አግልሎ ኢትዮጵያን ማዳን ከቶ አይቻልም። ስለዚህ ወቅቱ አብዝቶ  ከእያንዳንዳችን እላፊ አለመሄድን ይጠይቃል። በተጨማሪም እራስን አሸንፎ ሆኖ መገኘት ያስፈልጋል። እርስው እኮ እራስዎት አመለጠወት። ሰው መሆን በቂ ነው – ለዛሬም – ለነገም – ለነገ ተወዲያም። በበቀል ብቅል እዬታረሰ ያለውን የምልዕት መንፈስ መፈወስ የሚቻለው እርስው በመረጡት መንገድ አይደደለም። የድህንቱ መንፈስ እንዲህ ሲል ይቃኙታል http://www.zehabesha.com/amharic/archives/33615

ህዝባችን ጎጥ አስተዳደር እጅ እጅ ብሎታል።  እጅ እጅ ያለውን አስተዳደር የበቀል ብቅል ሚዛን ላይ አስቀምጦ ፍትሃትንት ማወጅ …. ቢደለዝ – ቢቀባባ – ቢሸፋፈን አይሆንም። ኢትዮጵያ ከትግራይ በወጡ ፈለፈሎች እዬተደበደበች ነው ያለችውልጆቿ መጠጊያ አልባ በቀን ብርሃን ጨለማ ተውጠው ነው ያሉት። በዜግነታቸው ለመኖር አልተፈቀደላቸውም። አልሰሙም ማለት ነው። የተከበሩ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ታላቅ እህት እኮ በ24 ሰዓት ሀገር ለቀው እንዲወጡ ነው የተበዬነባቸው … ምን ማለት ነው ይሄ …. የቀለም ጥልቅ ዕውቀተዎት ይህንን አምክንዮ እንዴት ይተረጉመዋል? እውነትና ሃቅን አይሸሹት! … ይድፈሩት! ….. ማነው የዜግነት ፈቃድ ሰጪው?! …. ሀገሬ ሰንድቅዓለማዬ ብሎ የማያውቅ የጎጥ አስተዳደር ….? ብዕረዎት ማጅራቷ ላይ ይሆን ዓይኗ ያለው? የጥበብ ሰው እኮ መከራን አብዝቶ መጋራት አለበት። መረመጥ አለበት። አልቻለችም ብዕረዎት …. ወንዝ መሻገር አቃታት …. ቃተተችም። የጥበብ ቋንቋ እኮ ሰውነት ብቻ ነው። የፍቅር መግለጫው ደግሞ ህግን አለመዳፍር ነበረ። ወደቀች አንዘላልጦትም። ወያኔ ማለት በግልጽ ቋንቋ ከባህር የወጣ አሳ ማለት ነው።

የኔዎቹ ወገኖቼ። እንደዚህ ዓይነት ክብሪት ብዕሮችና አንደበቶች አብረው የኖሩ ናቸው። በሰላሙ ጊዜ የተረጋጋ ተግባር ሲከውን ከቀፏቸው ውስጥ ተሰብስበው አድብተው ይቆያሉ። ወያኔ በወሰደው ጨካኝ እርምጃ ቁጣ ሲነሳ ግን አዲስ ተለጣፊ ነገር ፈብርከው ብቅ ይላሉ። መጠለያ አላቸው ድርጅት። ይህንንም መፈተሽ ያስፈልጋል። ማንዘርዘሪያ ማዘጋጀት በእጅጉ ያስፈልጋል።

እርግጥ ነው አንድ የፖለቲካ ድርጅት አባላቱ የሚተዳደሩበት ደንብ ለአባላቱ የህይወታቸው መተዳደሪያቸው ነው። ከዚህ ማዕቀፍ ከወጡ በድርጅቱ ሥርዓት ቅጣት ይፈጸምባቸዋል። እንደዚህ ዓይነት ሀገር የሚንድ ውጪ ያለነውን ሳይቀር ህግን ጥሶ ነፃነት የሚቀማ፤ ክብርን የሚዳፍር ተግባር አባላት ሲፈጽሙ ድርጅቶች ሃግ ማለት አለባቸው። በስተቀር ግን ተስማምተውበታል ማለት ነው።

በሌላ በኩል ድርጅቱን አትንኩ፤ የግል አስተያዬት ነው ለማለት የሚቻል አይመስለኝም። የፓርቲ አባል ትንፋሹ ከፓርቲው ማልያ ጋር የተሳሰረ ነው። በፓርቲ ህይወት ውስጥ ዬግል ዕይታ የሚባል ነገር የለም። በቀኝም – በግራም – በፊትም ሆነ በኋላም ቢመዘን – ቢፈተሽ በስተጀርባ ካላው የፓርቲውን አቋም ጋር እንደዚህ መሰል የአባላት ግድፈቶች ነፃ ሊሆኑ ከቶውንም አይችሉም። ነፃ ሊሆን የሚችሉት ፓርቲው በአባሉ ላይ ፈጣን  እርምጃ ሲወስድ ወይንም ግልጽ የሆነ አቋሙን በአደባባይ ሲገልጽ ብቻ ነው። በስተቀር ድርጅቱ አብሮ መድቀቁ የግድ ነው። አኔ ከፓርቲዬ – ፓርቲም ከእኔ ፈጽሞ መለዬት አይችልም። ምክንያቱም አንድ የፓርቲ አባልን ከፓርቲው ነጥሎ ለማዬት ፈጽሞ  አይቻልም። ሰርገኛ ጤፍ ላይ ነጭ ጤፍን ለቅሞ የማውጣት ያህል ከባድ ነው። ስለዚህ የእስካሁኑ ጉዞ በዚህ በተደባለቀ ዝንቅ ጉዙ ጊዜው መቃጠሉ አይደለም በጣም ብዙ ሀገራዊ ጉዳዮች ተጎድተዋል። ተመስገን! ሱማሌን መመከት በይቻል ዛሬ እንደ ህዝብና እንደ ሀገር ለመጠራት ባልቻልንም ርፍራፊ ነገር አለችን።

ከዚህ ባለፈ በዚህ መሰል የሀገር ጠላትንት ነቀዝነት ማጋዶዎቹ – ቅኖች – ደጎች – የእውነት አርበኞች – የግንባር ሥጋዎቹ አለፉ፤ ቤት ንብረት ፈረሰ፤ ልጆች ወላጅ አልባ ሆኑ፤ የሰው ልጅ እንደ እንሰሳ በመርዝ መሞከሪያ ሆነ …. በቤንዝንም ተቃጠለ … በጠራራ ጸሀይም በመዲናዋ የባሩድ እራት ሆኑ … በርካቶች ታፈኑ …. ከእንግዲህ ግን ዬሚከፈለው መስዋዕትና የትግሉ የጥራት ጉዙ መመጣጠን አለበት። ይህ የማግለል ዘመቻና ፖሊሲ የወያኔ ብቻ አይደለም አዲስ ነገር በቅሎ ለማዬት አይናቸው የማይችሉትም አቅም ቢሶች መገለጫ ነው። የሆነ ሆኖ የሾለከው ነጥሎ ሌላው ሾላኪውን እዬቀደሙ በጥንቃቄና በማስተዋል መጓዝን ይጠይቃል። ወቅቱ የመቆላማጫ የመላላሻ የጥሎሽ ጊዜ አይደለም።

…. ግን እንዲያው ለነገሩ ለእርሰዎ የተከበሩ ዬአቶ አንዳርጋቸው ጽጌ በመያዛቸው እንደዛ ሆነው በጎጥ አራዊቶች ማዬታችን፤ ወጣት ጀግኖቻችን የሃብታሙን፣ የዳንኤልን፤ የሽዋስን፤ የአብርሽን የጣር ድምጽ መሰማት እንዲህ ያስጨፍራል? ለእኔ አቶ አንዳርጋቸውን ጀግናዬም ሽልማቴም ብዬ መጻፌ ይህን ያህል ዛር ያስነሳል? ጎሽ ወያኔ ደግ አደረክ መልካም ሰራህ – የምትፈራውን ሰማዕት በእጅህ ስለገባልህ ሻማ ይብራልህ ልንል ነበር የተፈለገው …. ደግሞስ እኔ እኮ ነፃ ሴት ነኝ። የፈለግኩትን ድርጅት የመቀላቀል፤ የፈለኩትን ድርጅት ዬማድነቅና ዬማክበር፤ ውስጤ የሚያምንበትን አውጥቼ መጻፍ እንድችል እኮ ነው የተሰደድኩት። የእሶዎ አጋዚ ብዕር ተፈርቶ ጭጭ ረጭ እንዲባል ነበር የሚፈልጉት። እንዴት ተቀለደ?!

…. እጅግ የማከብራቸው ሙሴን ነው ወያኔ ያፈነው – የማድመጥ ሊቅም ነበሩ። ይውጣለዎት። ወያኔ ባንዳው ጠላቴ ነው። አሁንም ይደገም እስከ ማንፌስቶው መነቀል አለበት። www.tsegaye.ethio.info በዚህ ገባ ብለው „ተስፋ“ ላይ የድህረ ገጹን ዓላማ ያንብቡት ካስፈለገዎም በድምጽም ያገኙታል። በተጨማሪም እኔ ስላለኝ አቋም በዬ15 ቀኑ በዚህ በድምጽ ያገኙኛል እርግጥ አሁን የበጋ እረፍት ላይ ነን ግን አርኬቡ ላይ ያለውንም Radio Tsegaye Aktuell Sendung ገባ እያሉ ይኮምኩሙ።

ትናንት የተፈጠረች አይደለችም ሥርጉተ። እንዲህ ገባ ተብሎ የሚዘለልባትም አይደለችም። ነዳያንን ስንት ፍሪዳ አርደው ድንኳን ጥለው የልደት ፆምን አደግድግዎ ጉንብስ ቀና ብለው ከሚያስተናግዱ ሊቀ ሊቃውንታት የተፈጠረች ናት።  መንገድና መርህ ራይና ተስፋዋ ኢትዮጵያዊነት ብቻ ነው። በምንም ንቅዘትና ጸያፍ ተግባራትም ፈጽሞ የማትታሰብ ክውን ናት። እንዴት የምትደነግጣውን ሴት አግኝተዋል? እሷን አፍ ለማዘጋት – አይችሉም! – ህልም ነው! — ለመሆኑ ይህ ግራ በሚባለወስ ታላቁ መርህ „የሴቶች የእኩልነት የአርነት ትግል አልነበረንም? ምነው ግፊያ አሰኘዎት? አንዲት ሴት እንኳን ለማስተናገድ ታዬ አቅመዎት …. ትንሽ እራፊ ቦታ የለዎትም ለሴቶች ተሳትፎ …. እግዚኦ! አዬ አቅል – አዬ አቅል — አይገዛ ነገር ———–

በተረፈ የሀገሬ ጫካ ሆነ እስር ቤቱንም የማውቀው ነው። ለእኔ አዲስ ዬሆነ ነገር የለም። ምነው ወጣት በሆንኩ በነበረ እንዲህ የዘር ዛርን በብዕር ሳይሆን በባሩድ ነበር የማሰተነፍሰው በለመድኩት ጫካ።

የኢትዮጵያ ወቅታዊ የመወያያ ክፍል መድረክን  በሚመለከት በእኔ ሥም አይወርፉት። እኔ አድሚንም ቦርድም አባል አይደለሁም። በህግ ዕውቅና ያለው የተደራጀ ስለሆነ ዕውቅና የሰጠው አካል ቢጠይቀዎት መልስዎት ምን ይሆን? በቃ ቱግ – ቱጉ ብቻ … ማህከነ!

ከረንትን ያህል ኢትዮጵያዊ ተቋም በቦርድ አባልነት ለመምራት አቅሙ የለኝም። ቢሆን ግን ደስታውን አልችለውም። እርግጥ ነው ከዬካቲት 2009 አስከ የከቲት 8 . 2010 ቋሚ አባል ነበርኩኝ። አሁን አባል ባልሆንም እናት ቤቴነቱ ግን እንደተጠበቀ ሆኖ የድህረ ገጹ ደግሞ ዘበኛው ነኝ። የማይመቸኝ ላይ ሚዛን ለመጠበቅ ብዙ ጊዜ ከሥር እጽፋለሁ። አላምነውም በቀን እስከ ስድስት ጊዜ አዬዋለሁ። ይገርመወታል ሌሊት ሁሉ ክፈት አድርጌ አዬዋለሁ። እንደ ጦር የምትፈሩት የተግባር ቤት ስለሆነ ነው። ከረንት አቅሙን የሚገልጸው በሥራ ነው። አቋሙ ደግሞ ከጊዜ ጋር እንደ ወጀብ እንደነካው ዛፍ አይዘፍንም። ቀጥ ያለ የአደራ ማውጫ ቤት ነው። ኢትዮጵያዊነትን ሰንደቁ ስላደረገ ትቢያ ለበሳችሁ አፈር ቆረጠማችሁ ብትረግሙትም ከተግባሩ አንድ ጋት ፈቅ እንደማይል አስባለሁ። ግልጽና ጽኑ አቋም ነው ያለው። አቋሙ ወያኔ ከነጉቱ ከነ ዘረኛ ማኒፌስቶው መነቀል አለበት ባይ ነው። ይህ ደግሞ የእኔም የህይወቴ መርህ ነው ተግባባን ጌታው?!።

ማይጨውን ሳዬው ደግሞ …  ዬሽበት ትርጉሙ ሽሽጉኝ ብሎ ጆንያ ውስጥ ሲቀረቀር አዬሁት። ታዬኝ እኮ ማይጮ የግንቦት 7 አባል ሲሆን? በመንፈሱ የጉልማ መሬት ታህል ለትጥቅ ትግል ቦታ እንዳልነበረው ነበር እኔ ሳውቀው። ሰላማዊ ትግል ደጋፊ ሆኖ ነው እኔ የማውቀው። ኢሳትን ሊደግፍ ይችላል – የነፃነት ትግሉ መተንፈሻ ንጹህ ቧንቧ ስለሆነ። ይህ ደግሞ ለወያኔ ስርዎ ስውርም ደጋፊዎች ረመጥ ነው። ቅጥል – ድብን  - ፍርክርክ አድርጎ ብርክ ያስይዛችኋል።  እኔ እንደማስበው ያው እርስዎም ተደብቀው ያጣጥሙታል ብዬ አስባለሁ። ያው ቅናት ናት እንዲህ ፈርፈር የምታደረግዎ እንጂ። በልበዎ ያደንቁታል አይደል ኢሳትን? ማንም የአፍሪካ ሀገር ያልደረሰበት የእድገት ደረጃ ላይ ስደት ላይ ሆኖ ተግባሩ አንቱ ነው።

ሳረሳው ደግሞ አንድ ነገር – አልኮዎት ጌታው አሁን እኔ ሌላ የወመኔውን ድራማ እዬጠበኩ ነው። … ኢሳትን የሚረዱት ጥንታዊ ጠላቶችችን ናቸው የሚል …. ይህ አይቀሬ ነው። ለነገሩ እርሰዎም እኔም ተሰደን የምንኖርባቸው ሐገሮች አንድም ቀን ለአፍሪካ የነፃነት ትግል ቀን ያወጣቸው ዬሀገረ – ኢትዮጵያ ወዳጆች አይደሉም። ማንስ ወዳጅ ኖሯት ሲያውቅ ነውና? ስለዚህ እርስዎም እኔም ጓዛችን ጠቅለላ ነዋ ከእነሱ ዘንድ አይደለን ያለነው? በፈለገው ቅርጽና ይዘት ብቅ ይበል  ዬእንኮሸሽሊቱን* የበቀል ብቅሉ ድራማ እንኩቶ እናዳርገዋለን። አይገርመንም – አይደንቀንም። አሁንስ ተግባባን?! … ያው ያችን አንጠልጥሎ ማቀጣጠያ የባህር ዛፍ ቅጠል ለቀማ ቢወጣ ባዶ እጁን ተመላሽ ይሆናል – ግፋፎው – ወያኔ። ሌላው እርስዎም አንደሚያውቁት  ዘረኛው ወያኔ የሚተነፍስው በልምና ስንዴ ነው እንኳንስ የስደቱ ሚዲያ …. ስለዚህ ገና ወያኔ አፉን ሲከፍት ቆረቆንዳ በልኩ ተሰርቶለት ይደፈናል – እሺ!

ሲገርሙ! ምነው ይህቺ ሚዛኗ ላይ አስኳላዋን ገፋ አላደረጉ ይሆን? ሰው በነፃነት በሚኖርበት ሀገር ካላፈቃድ ፎቶ በወንጀለኛ ሥንኝ … መለጠፍ፤  እንደ ተቋም ሶስቱም ሩሞች ህግ በመተላለፍ ክስ ቢመሰርቱ ዋጋወን ያገኙ ነበር። ታዳሚውን ሁሉ እኮ ነው አብረው ያረሱት። ኦኦ!  በግለሰብ ደረጃም ቢሆን ፎቶና ከሥሩ የጨነቆሩት ሐረግ በራሱ ገመድ ነበር አዙሮ የሚያንቅዎት። በጣም ተዳፈሩ፤ በጣም እራስዎትን ውድና ዬትግራይ ህዝብ ተቆርቋሪ አደረጉ፤ ቆርጠውና ቀደው የሚያሳድሩን ያህል ነው የተጋፉት፤ ግን ህግ እዬተላለፉ – እዬዘለፉ – እያዋራዱ …. እንዴት እንቅልፍ ወሰዶዎት?

ለመሆኑ „ናዚ“ ማለት ምን ማለት ነው? እንዴትስ በምንስ ሁኔታ ሊከሰት ይችላል? አስፈጻሚ ተቋማቱ ምንድን ናቸው? ዬዶክተሪኑ ሥነ ህይወት ገጽታ ሆነ ፍለስፍናው በምን ይገለጻል? በዚህ እድሜ -  በዚህ የዘመናት ተመክሮ በስሜት የተከዘነ ጆንያ ሙሉ የጭድ ትንፋሽ የኢትዮጵያን የነፃነት ራህብ አይታደግም። ዙሪያ ገባው ነዳላ – መወተፊያ ወይንም መጥቀሚያ መርፌ ወይንም ለማያያዝ ሙጫ ነገር የማይደፈረው  የተቆራረጠ ሙጣጭ – ግብና መቋጠሪያ አልቦሽ ኩረት ነው ሲደረደሩ እንቅልፍ አልባ ሆነው የሰነበቱት ….

ጌታው አንሰነባበት – ስንብቱ ለዳርቻ ነው። ከዚህ በኋላ የገደሉትን ገድለው – የወቁትን ወቅተው – ቀረኝ የሚሉት ማሳ ካለዎት ያስኬዱት። የፈራን እንዳይመስለዎት። ከትጋታችን አንዲት ጋት ፈቅ የማንል እንደሆነ እንዲያውቁት ነው የተጣፈለዎት። ቀጣዩ ህይወትዎትን – ዘርዎትን ፍለጋ መማሰን ሽበትዎትን – ዝልቅ ተመክሮዎት አንገቱን ደፍቶ እዬጠበቀዎት ነውና ይታረቁት። የሽንፍላ ጹሑፎወትን የመረጃ ማያያዣ ሊንከዎትን አለጠፍኩትም ተጸዬፍኩት – ገዳይ ገዳይ ወይንም አስገዳይ አስገዳይ ይሸታልይከረፋል። እኔ አብቅቻለሁ። መልካም የምንም ጊዜ …..

ውዶቼ የእኔዎቹ አሻቅቦ በሁሉ ነገር የሚበልጥን ወገን መናገር እንዴት ይከብድ ይመስላችኋል። ያልኖርኩበትና ያላደኩበት ሆኖ ውስጤን አብዝቶ አስጨነኩት። ግን መሆን ነበረበት። የኔዎቹ ደህና ሰንብቱልኝ። መሸቢያ ጊዜ! ውድድድ.

 

  • ጉርና – የቅል ዕድገት ማብቂያ – ቅርጽ የለሽ ዕድገቱ አንገቱን ውጦ ሽንጡን ያሰፋዋል። በባለሙያ ውስጡ በሚገባ ይዘጋጅና ማንገቻ ይሠራለታል። ከባላ መንታ እንጨት ላይ ሆኖ እርጎ ይገፋበታል ወይንም እርጎው ተንጦ ቅቤ እንዲወጣ የሚረዳ ባህላዊ ዕቃ ነው። ትንሽ የምትሉት ብዙ ስለሚይዝ ጉርና ይመስል ሆድ አታብዛ ይባላል። ከተሰጠው ጸጋ ወጥቶ እሳት ላይ ቢጣድ ግን ከማረርም አልፎ ከእርጎ ጋር ጎርንቶ ተነዳድሎ እራሱ ህልፈቱን ያውጃል።
  • ኩታራ - የልጅነት ጊዜ። ምራቁን ለዋጠ የእድገት ደረጃ ገና ጮርቃ የሆነ እንደ ማለት።
  • እንኮሸሸሊት - ቅጠሉም ግንዱም ፍሬውም እሾህ የሆነ በወይና ደጋ የሚበቅል የዕጽዋት ዓይነት

 

 

ለእኔስ ሰው መሆኔ ብቻ ይበቃኛል!

ኢትዮጵያዊነት ፈተናን አሸንፎ የተፈጠረ ሚስጥር ነው!

ደሜን ሳደምጠው ውስጤን አገኘዋለሁ!

 

 

 

 

 

፪፭ኛ ዓመት በአለ ሢመት እና የመንበረ ፓትሪያርክ ጽ/ቤት ምረቃ

ኢትዮጵያዊነት ማለት

0
0

አንዱዓለም ተፈራ (እስከመቼ) 

“ኢትዮጵያዊነት ማለት፤ ኢትዮጵያዊያንን መውደድ፣ ኢትዮጵያን ማፍቀር፤ የኢትዮጵያን መንግሥት በተገቢው መንገድ መደገፍና፤ ይህ መንግሥት የተሳሳተ መንገድ ሲይዝ መቃወም ማለት ነው። በሥልጣን ላይ ያለው ክፍል ፀረ-ኢትዮጵያዊያንና ፀረ-ኢትዮጵያ ሲሆን፤ ያንን ክፍል በማንኛውም መንገድ ማስወገድ፤ የያንዳንዱ ኢትዮጵያዊና የያንዳንዷ ኢትዮጵያዊት፤ ኢትዮጵያዊ ግዴታ ነው።”

አብዛኛዎቻችን በየጊዜው የምናነሳው ጉዳይ፤ ሀገራችን ኢትዮጵያ ያለችበትን የፖለቲካ ሀቅና በኢትዮጵያ ሕዝብ ላይ እየደረሰ ያለውን በደል ነው። ኢትዮጵያዊ ነኝ ወይንም አይደለሁም የሚለውን ጥያቄ አይደለም። በየቦታው፣ በተገኘው አጋጣሚ፣ በየዕለቱ በሕዝቡ ላይ የሚደረገውን በደል እናውጠነጥናለን። ኢትዮጵያዊያን ናቸው ወይንም አይደሉም የሚለው ከጥያቄያችን መካከል አይደለም። መቼም አርባ ዓመት ሙሉ፤ በአረመኔው መንግሥቱ ኃይለማርያምና በወገንተኛው የትግሬዎች ነፃ አውጪ ግንባር መንግሥት፤ በኢትዮጵያ ህዝብ ላይ የደረሰውን ግፍና በደል ገና ብዙ ፀሐፊዎች ብዙ ይውሉበታል፣ ሊቃውንት ይቀኙበታል፣ አንጎርጓሪዎች ይደረድሩበታል፣ ሰዓሊዎች ያቀልሙታል፣ ገጣሚዎች ይሰነኙበታል፣ መጽሐፎች ይደረሱበታል። ያ ግን፤ ከኛ ቀጥለው የሚመጡት ኢትዮጵያዊያን፤ ስለኛ ስለቀደምናቸው ኢትዮጵያዊያን ለማወቅ የሚያደርጉት ጥረት ውጤት ነው እንጂ፤ ኢትዮጵያዊ ስለመሆናችን ወይም ኢትዮጵያዊ ስላለመሆናችን አይደለም።

እንግዲህ የአሁኑ ሰዓት ኢትዮጵያዊነት ምንድን ነው? የሚለውን በደንብ መረዳት አለብን። ይኼን ስናደርግ፤ የሀገራችንን የኢትዮጵያን የፖለቲካ ሀቅ በትክክል እንረዳና፤ በኢትዮጵያዊነታችን፤ ምን ማድረግ እንዳለብንና ማን ኢትዮጵያዊነቷን እየተወጣች እንደሆነች እንገነዘባለን። ትናንትም፣ ዛሬም ነገም ኢትዮጵያዊነት ማለት፤ ኢትዮጵያዊያንን መውደድ፣ ሀገርን ኢትዮጵያን ማፍቀር፤ የኢትዮጵያን መንግሥት በተገቢው መንገድ መደገፍና፤ ይህ መንግሥት የተሳሳተ መንገድ ሲይዝ መቃወም ማለት ነው። በሥልጣን ላይ ያለው ክፍል ፀረ-ኢትዮጵያዊያንና ፀረ-ኢትዮጵያ ሲሆን፤ ያንን ክፍል በማንኛውም መንገድ ማስወገድ፤ የያንዳንዱ ኢትዮጵያዊና የያንዳንዷ ኢትዮጵያዊት፤ ኢትዮጵያዊ ግዴታ ነው። ወራሪ ሆኖ ሲገኝ ደግሞ፤ ይህ ግዴታ፤ ወደ መኖር ወይንም አለመኖር የሕይወት ትንቅንቅ ስለሚያመራ፤ አማራጭ የማይሠጥ ጥሪ ይሆናል። ይህ ፖለቲከኛ መሆንን ወይንም አለመሆንን አይጠይቅም። ይህ ታጋይ መሆንን ወይንም አለመሆንን አይጠይቅም። ይህ ሀገራዊ ግዴታን ነው የሚገልጸው። ይህ የኢትዮጵያዊ ሕይወት፣ የትናንት፣ የዛሬና የነገ ሕልውና ጥያቄ ነው። አሁን በሀገራችን በኢትዮጵያ ውስጥ፤ ኢትዮጵያዊ መንግሥት የለም። ሕግና ሥርዓት የሚያከብር ቡድን አይደልም በሥልጣን ላይ ያለው። ራሱ የሚያወጣቸውን ሕጎች የሚያፈርስ፤ ኢትዮጵያዊነትን ለማጥፋት የተነሳ ክፍል ነው በሥልጣን ላይ የተቀመጠው። ኢትዮጵያዊያንን እየከፋፈለ፣ አንድነት እንዳይኖረን የሚጥር መንግሥት በሥልጣን ላይ አለ። የኢትዮጵያ ሕዝብ ደግሞ፤ “ኢትዮጵያዊ ነኝ። አልከፋፈልም። ጠላታችን የትግሬዎች ነፃ አውጪ ግንባር መንግሥት ነው።” እያለ ትግል ይዟል። ስለዚህ፤ የአሁኗ ኢትዮጵያዊትና የአሁኑ ኢትዮጵያዊ፤ ኢትዮጵያዊ ግዴታችን፤ ይኼን ፀረ-ኢትዮጵያዊያን መንግሥት ከታጋዩ ህዝብ ጎን ተሰልፎ ማስወገድ ነው። ሕዝባዊ ንቅናቄ ከፊታችን ተደግኗል። የውዴታ ሳይሆን ግድ ሆኖብን፤ የምርጫ ሳይሆን አማራጭ ሳይኖረን ንቅናቄው አፍጥጦብናል። የዴሞክራሲ ቅንጦት ሳይሆን የሀገር አድን ጥያቄ ቀርቧል።

ባጭሩ ኢትዮጵያዊነት ማለት፤ የኢትዮጵያ ጠላት የሆነውን ወራሪ መንግሥት ማወገድ ነው። ይኼን የኔ ብሎ ያልተነሳ ግለሰብ፤ ኢትዮጵያዊነቱ ምኑ ላይ ነው? በርግጥ ትግሉ ረጅም ነው። ትግሉ የተመሰቃቀለ ነው። በሥልጣን ላይ ተቀምጦ ፀረ-ኢትዮጵያዊነት ፍልስፍናውና መመሪያው የሆነው የትግሬዎች ነፃ አውጪ ግንባር ብቻ ሳይሆን፤ ይኼኑ ፍልስፍናና መመሪያ የራሳቸው ያደረጉ ሌሎች ክፍሎችም የኢትዮጵያዊነት ትግላችን አንድ ክፍል ናቸው። በትግሉ ውስጥ ያለን ኢትዮጵያዊያን በሙሉ ይኼን ሀቅ አጥብቀን መያዝ አለብን። ኢትዮጵያ ለዘመናት መንግሥት ኖሯት ስትተዳደር የነበረች ሀገር ለመሆኗ አጥጋቢ መረጃዎች አሉ። እኒህ መንግሥታት በየተከሰቱበት የታሪክ ወቅት፤ በጎም ሆነ በጎነት የጎደለው ተግባር አከናውነው አልፈዋል። በዚህ ረጅም ታሪካችን፤ የመንግሥታዊ ማዕከላቸውን በሰሜን ወይንም በደቡብ፤ በምሥራቅ ወይንም በምዕራብ እንደታሪካዊ ወቅቱም ተንቀሳቃሽ በማድረግ፣ የተለያዩ የጦር አሠላለፍን በማዘጋጀት፣ ጥንካሬያቸው እንደፈቀደላቸው፤ የሀገሪቱንም ደንበር ሲያሠፉና ስትጠብባቸው ነበር። አንዱ ከሌላው ጎጥ፤ ሃይማኖት ሳያግደው፣ የዘር ሐረግ ሳይከለክለው፣ እንደ ጥንካሬያቸውና የፖለቲካ ግኘታ አመቺነታቸው ሲጋቡና ሲዋለዱ ነበር። በኢትዮጵያዊነት ገዝተዋል። እናም በተለያዩ ጊዜያት፤ በተለያዩ መንግሥታት ዘመን፤ የተለያዩ ህዝባዊ ጥያቄዎች ተነስተዋል። ሕዝባዊ አመፆች ተካሂደዋል። መፈንቅለ መንግሥት ተደርገዋል። በንጉሥ ላይ ንጉሥ ተነስቷል። ንግሥታት ዘውድ ጭነው ገዝተዋል።

የውጭ ሀገር ጉልበተኛ መንግሥታት ሀገራችን ጠንካራ ማዕከላዊ መንግሥት እንዳይኖራት የተጫወቱት ሚና ቀላል አይደለም። እንዲያውም ከሞላ ጎደል የሀገራችን የኢትዮጵያ ታሪክ፤ ከውጭ ወራሪዎችና ጣልቃ ገቦች ጋር የመኖርና ያለመኖር ተጋድሎ ነው ብሎ ማስቀመጥ ይቻላል። አሁንም የውጭ ኃይላት ለጥቅማቸው ሲሉ ያላቸው እርጎ ዝምብነት ትልቁ በሽታችን ነው። አሁን በውጭ የምንገኝ ኢትዮጵያዊያን በጠቅላላው በውጭ ሀገር መንግሥታት ላይ ልናደርግ የምንችለው ጫና ወይንም ቀና አመለካከት እንዲኖራቸው የምናደርገው ጥረት፤ የትም አይደርስም። ይልቁንስ በራሳችን መካከል ያለውን ጥንካሬ በአንድነት በመሰባሰብ ብናጎለብት፤ እኛ ወደነሱ ለአቤቱታ ከመሄድ፤ እነሱ ወደኛ ለጥቅማቸው የሚመጡበትን መንገድ እንፈጥራለን። የሚረዱት ቋንቋ፤ የራሳቸው ጥቅምና የኛ ጥንካሬ ብቻ ነውና! ሆኖም ወደኛ ስንመለስ፤ በዚህ በሀገራችን የታሪክ ጉዞ፤ ኢትዮጵያዊነት በጥያቄ ውስጥ ገብቶ አያውቅም። ለምን?

አንድ ግለሰብ በመንግሥት ውስጥ የያዘው የሥልጣን ደረጃ፣ ያለበት ድርጅት አባልነቱ፣ የተወለደበት አካባቢ፣ የሚናገረው ቋንቋ፣ ያለው የሀብት ብዛት ወይም ማነስ፣ የትውልድ ሐረጉ መሠረት፤ የግለሰቡ ብሶት ወይም ምቾት፤ ይህ ሁሉ አንድን ኢትዮጵያዊ ከሌላዋ ኢትዮጵያዊት ያነሰ ወይንም የተለቀ ኢትዮጵያዊ አያደርግም። ሁላችን ኢትዮጵያዊያን፤ በአንድነት ሙሉ ኢትዮጵያን እንጋራታለን። የጋራ ሀገራችን ናት። የነበሩት፣ ያለነውና የሚመጡት ሁላችን በአንድነት ባለቤቶች ነን። አንድ የተቧደነ ክፍል፤ በመንግሥት ደረጃ ሥልጣን ላይ ወጣም ወይንም በተቃውሞ አፈነገጠ፤ የኢትዮጵያ ግለኛ ባለቤት ወይንም የኢትዮጵያዊነትን ትርጉም ሠጪና ነሽ አይደለም። ይህ ደግሞ ነገሥታትንና ማንኛውንም በሥልጣን ላይ የሚወጣን ክፍል ይጨምራል። ኢትዮጵያዊነት በሥልጣን ላይ የሚወጣው መንግሥት ወይንም አንድ ጅንን ግለሰብ ትርጉም የሚሠጠው ጉዳይ አይደለም። ኢትዮጵያዊነት ከዚያ በላይ ነው። የታሪክ ትስስር ነው። እትብት ነው።

አይደለሁም ብሎ እስካላፈነገጠ ድረስ፤ አንድ ግለሰብ፤ ኢትዮጵያዊ ሆኖ በመወለዱ ኢትዮጵያዊ ነው፤ ወይንም የኢትዮጵያ ዜግነት አለው። ኢትዮጵያዊነት የሀገረ ኢትዮጵያ ዜጋ ሆኖ መገኘት ነው። ኢትዮጵያዊነት በዜግነት ላይ የተመሠረተ የግለሰብ ሀገራዊ መብት እንጂ፤ የስብስብ ወይንም የአካባቢ ጥምር መብት አይደለም። “በግል ወይንም በአካባቢ በደል ደርሶብኛልና ኢትዮጵያዊነት ለኔ ምን ያደርግልኛል?” የሚለው አባባል፤ በቀላሉ ሲታይ የየዋህነት አለዚያ ደግሞ የመሠሪነት ገጽታ ነው። መገንዘብ ያለብን፤ የትግሬዎች ነፃ አውጪ ግንባር መሠረት አድርጎ የተነሳው፤ በራሳቸው መሥራችና የጦር መሪ አረጋዊ በርሄ እንደተገለጸልን፤ አፄ ሚኒሊክ የጣሊያንን ወራሪ ጦር ለማባረር ትግራይ ሲሄዱ፤ ለወታደሮቻቸው ምግብ እንዲያቀርብ፤ የትግራይን ገበሬ ስላዘዙት ነው። እናም ሀገርን ከወራሪ ለማዳን የዘመተን ጦር መመገብ በደል አድርገው ቆጥረው፤ የዛሬዎቹ ገዝዎቻችን ተስባስበው ደደቢት ገቡ። ኢትዮጵያዊነት ገደል ይግባ አሉ። አሁንም በደደቢቱ ግንዛቤያቸው ኢትዮጵያን ወረዋል። መንግሥታቸው ኢትዮጵያዊ አይደለም። ሌሎችን በሚመለከት፤ እስኪ አስቡ፤ በደል አለብኝ ባይ ኢትዮጵያዊነቱን በጥያቄ ውስጥ ካስገባ፤ ከትግሬዎች ነፃ አውጪ ግንባር ምን ለየው?

“ኢትዮጵያዊ አይደለሁም፤ ሌላ ነኝ።” ማለት፤ የግለሰብ መብት ነው። ያ በግል፤ አንድ ግለሰብ፤ ለራሱ ለግለሰቡ የሚሠጠው ዜጋ የመሆን ወይንም ያለመሆን ጉዳይ እንጂ፤ አንዱ ለሌላው ሊሠጠው ወይንም ሊነፍገው የሚችል ዜግነት አይደለም። በመንግሥት ደረጃ፤ ትክክለኛውን የሀገሪቱ ሕገ መንግሥት በመከተል፤ ለአዲስ አመልካቾች ዜግነት ሊሠጥ ወይንም ሊነፈግ ይቻላል። ኢትዮጵያዊ የሆነውን ዜጋ ግን፤ በምንም መንገድ ኢትዮጵያዊ አይደለህም ሊል የሚችል ማንም የለም። ግለሰብ ኢትዮጵያዊ ሲያጠፋ በሕግ ይጠየቃል። ፀረ-ኢትዮጵያ ተግባር ሲሠራ ደግሞ፤ በከሃዲነቱ ባንገቱ ላይ ሽምቅቅ ያርፍበታል። ሀገር አስመስጋኝ ተግባር ሲፈፅም፤ የሀገር ታዋቂነትን ያገኛል። ኢትዮጵያዊነት ይህ ነው። በወራሪ መንግሥት ላይ ማመጽ፤ አርበኝነት እንጂ፤ ወንጀል አይደለም። ይህ ለግለሰብ ብቻ ሳይሆን፤ ኢትዮጵያዊ ለሆኑ ተቋማትም ይሠራል። አስመስጋኝ ተግባር ሲያከናውኑ፤ ሀገራዊ ታዋቂነት ይሠጣቸዋል። ፀረ-ኢትዮጵያ ሲሆኑ ይዘመትባቸዋል። እንደግለሰቡ ሽምቅቅ፤ ለተቋማቱ ደግሞ ፍፃሜያቸውን የሚያገኙበት ክንውን ይደረጋል። መንግሥትም ሀገራዊ ተቋም ነው። የትግሬዎች ነፃ አውጪ ግንባር መንግሥት ፀረ-ኢትዮጵያ ነው። እናም ፍፃሜውን ማምጣት፤ ኢትዮጵያዊ ግዴታችን ነው።

“እኔ አንድ ግለሰብ ነኝ። ምን ማድረግ እችላለሁ?” በማለት ኢትዮጵያዊ ኃላፊነታችንን ከኛ ማራቅ አንችልም። ኢትዮጵያዊነት አንዴ የሚመጣ ሌላ ጊዜ ደግሞ የሚሸሽ ጥላ አይደለም። ሁሌም አብሮን አለ። በደማችን ውስጥ ፈሳሹ፣ በአጥንታችን ውስጥ ጽናቱ፣ በቆዳችን ላይ ሰብሳቢ ክኑ ነው። በድርጅት ተሰባሰብን ወይንም የመንግሥት ሠራተኛ ሆን፤ ኢትዮጵያዊነታችን አይለወጥም። ኢትዮጵያዊነትን ከኢትዮጵያዊነት ውጭ ሆነን የምንጠይቀው ጉዳይ አይደለም። ነን ወይንም አይደለንም? ብቻ ነው መለኪያው። ግማሽ ኢትዮጵያዊ የለም። ሩብ ኢትዮጵያዊት የለችም። “ቆይቼ እሆናለሁ አሁን ተበድያለሁ።” ብለን በቆይታ የምናስቀምጠው ጉዳይ አይደልም። በደል ሌላ! ማንነት ሌላ!

እኛ አሁን ኢትዮጵያዊያን ነን ብለን፤ በዚህ በዘመናችን የኖርንበትና የምንኖርበት፤ ኢትዮጵያዊ ኃላፊነታችንን አስመልክቶ፤ ምን እያደረግን ነው? የሚለው ደግሞ የዛሬ ጥያቄ ነው። በመካከላችን የተለያየ መልስ የምንሠጥ አለን። ከነዚህ መካከል በዚህ በያዝነው ወቅት ነበርን ለማለት የሚያስችል ምልክታችን ምንድን ነው? የወቅታችን ማመልከቻ ሆኖ የሚታየው፤ አንድም በደሉን በመፈጸም የተሠለፉት ጥቂት የሥልጣን ጥመኞች እና በዝርፊያ በሕዝቡ ገንዘብ ለግላቸው የገነቧቸው ሕንፃዎች ሲሆኑ፤ ሌላ ደግሞ እኒህን ሲታገሉ ሕይወታቸውን ለሕዝቡ ድል የሠጡት ናቸው። በመካከል የሠፈርነው ከሞላ ጎደል ብዙዎቻችን፤ እድሜያችንን ቆጥረን ከማለፍ በላይ የምናስመዘግበው የለንም። በእርግጥ ትግል ተደራጅቶ ነው። ብዙ የሚታገሉ ድርጅቶች አሉ። የድርጅቶቹ ታሪክና የአሁን ሁኔታ ደግሞ አያስመረቃም። ነገር ግን ሌሎቻችን እጅና እግሮቻችንን አጣጥፈን በመቀመጥና “እነሱ” እያልን ተደራጅተው በሚታገሉት ላይ እጣቶቻችንን በመቀሰር፤ ከኢትዮጵያዊ ኃላፊነታችን ነፃ መውጣት አንችልም። ድርጅት መኖሩ ታጋዮች የሚያደርጉትን ጥረት አመልካች ነው። ከነዚህ ጋር መተባበር ካልቻልን፤ ድርጅቶቻቸውን እንደጣዖት የሚያመልኩና ከሀገራቸው ከኢትዮጵያ የሚያስቀድሙ ከሆነ፤ ሌሎችን በማስተባበር እንዲስተካከሉ የማድረጉ ኃላፊነት ከራሳችን አይወርድም። ድርጅት ምክንያት ሆኖ ከኢትዮጵያዊ ኃላፊነታችን ነፃ አያወጣንም። እነ ርዕዩት ዓለሙ፣ እነ አንዱዓለም አራጌ፣ እነ እስክንድር ነጋና የእስልምና እንቅስቃሴው ተወካዮች፤ የድርጅት አባል ስለሆኑ ወይንም ስላልሆኑ አይደለም የታሠሩት። ግለሰቦቹ እንጂ ድርጅት አይደለም የታሠረው። የታሠሩት ኢትዮጵያዊ መብታቸውን ስለጠየቁ፤ በሥልጣን ላይ ያለውን ፀረ-ኢትዮጵያ ወገንተኛ የትግሬዎች ነፃ አውጪ ግንባር መንግሥት በመቃወማቸውና ለገዥው ክፍል ጉቦም ሆነ የገጠጠ እብሪት አንገታቸውን ባለመድፋታቸው ነው። ባጭሩ ኢትዮጵያዊ ሆነውና ኢትዮጵያዊ ኃላፊነታቸውን እየተወጡ በመገኘታቸው ነው።

ታዲያ እንዲህ ያሉ ታጋዮች በእስር ቤት በሚማቅቁበት ወቅት፣ አብዛኛው ሕዝብ እንደሁለተኛ ዜጋ በሚንገላታበት ሀገር፣ መሳደዱና መገፋቱ ሀገርን እንደ የእሳተ ጎመራ ግንፍል እየሮጡ ለማምለጥ ብዙዎቹ በሚሽቀዳደሙበት ጊዜ፣ ኢትዮጵያዊ ኃላፊነታችን ምን እንድናደርግ ያስገድደናል? በድርጅት ዙሪያ የልተካተቱ ግለሰቦች በተደጋጋሚ ከሚሠጧቸው ምክንያቶች አንዳንዶቹ እኒህ ናቸው፤

“ድርጅት ለኔ አይመቼኝም። ሃሳቤን በነፃ የማካፍልበትን መድረክ ብቻ ነው የምፈልገው።

“ድርጅት ለኔ አልጣመኝም። ከዚህ በፊት የነበረኝ ተመክሮ አስቸጋሪ ነበር።”

“እኔ ሌሎች ወደ ተግባር እንዲሄዱ በሃሳብ ልረዳ እችላለሁ።”

“የትግል ማዕከል እኮ የለም። የተያዙት መሥመሮች በሙሉ ትክክል አይደሉም።”

“እኔ በሰብዓዊ መብቶች ረገጣ ዙሪያ እየሠራሁ ነው።”

“ድርጅቶች እኮ የሚረቡ አይደሉም። እውነተኛ ድርጅት የት አለና!”

“ትንሽ ጊዜ መቆዬት እፈልጋለሁ።”

የሚሉት ናቸው። እኒዚህና የመሳሰሉትን በመደርደር ከኢትዮጵያዊ ግዴታ ለማምለጥ መሞከር ሀቁ ምንድን ነው? በተለይ በአሁኑ ሰዓት! በየጊዜው የሀገራችን የኢትዮጵያንና የህዝቧን ሁኔታ እያነሳን፤ በብዙ የመገናኛ መንገዶች ሁሉ ጽፈናል፣ ተርከናል፣ አንብበናል፣ ተንትነናል። አሁን በያዝነው መንገድ እየተጓዝን የትም አንደርስም። ተባብረን መታገል ያለብን መሆኑ ግልጽ ነው። ዋናው “ሌሎች ይተባበሩ!” “ድርጅቶች ይተባበሩ!” “ህዝቡ ይተባበር!” ማለቱ አይደለም። እኛስ በግለሰብ ደረጃ የምንገኝ ኢትዮጵያዊያን ምን ኃላፊነት አለን? እያልን ራሳችንን መጠየቅ አለብን። ሀገራችን ለሁላችን እኩል ናት። መደራጀታችን ወይንም አለመደራጀታችን ያነስን ኢትዮጵያዊያን አያደርገንም። የሀገራችን ችግር የተደራጁ ኢትዮጵያዊያን ችግር ብቻ አይደለም። ታዲያ ኃላፊነቱን እኩል መካፈል አለብን። እናም እኛስ ምን እንደርግ? ብለን ራሳችንን መጠየቅ አለብን። እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ እና እያንዳንዷ ኢትዮጵያዊት፤ ተደራጁም አልተደራጁም እኩል ኃላፊነት አለብን። እናም እያንዳንዳችን መፍትሔ ፍለጋውና የመፍትሔው አካል መሆኑ ላይ፤ እኩል ድርሻ ሊኖረን ይገባል። ይህ የሀገር አድን ወቅት ነው።

ትግሉ የራሱ የሆነ ዕድገት ያለው፤ ሕጉ የማይታወቅበት ሂደት ነው። አሁን በረጋ መንፈስ ባጭር ጊዜ ውስጥ በቀላሉ የምንችለውን የትግል ማዕከል የመፍጠር ሂደት ብናዘገየው፤ ተቀምጠን የተውነውን ቆመን የማናገኝበት ጊዜ ይመጣል። ዛሬ በግልፅ መነጋገር፣ መሰባሰብና ትግሉን በአንድነት ማድረግ ካልቻልን፤ ነገ ይኼ መሰባሰብ ላም አለኝ በሰማይ ይሆንና ቁጭቱ፤ ድሮ ነበር እንጂ መጥኖ መደቆስ አሁን ምን ያደርጋል ወጪት ጥዶ ማልቀስ፤ ይሆንብናል።

ለድርጅቶችም ሆነ ለግለሰቦች አሁን ኢትዮጵያዊ ጥሪው፤ አንድነት በኢትዮጵያዊነታችን እንድንሰባሰብ ነው። የምንሰባሰበው ለወገናችን ለመድረስ፣ ሀገራችንን ነፃ ለማውጣት ነው። የምንሰባሰበው በኢትዮጵያዊያን የነፃነት ንቅናቄ እንዋቀራለን። ይህ የትግሉ ማዕከል ይሆናል። ይህ የነፃነት ንቅናቄ፣ የትግሉን ራዕይና ተልዕኮ በግልፅ አንጥሮ በማውጣት፤ በአደባባይ ሕዝባዊ ንቅናቄውን ይመራል። ይህ ማዕከል፤ ለኢትዮጵያ ህዝብ በየቦታውና ባመቸው መንገድ፤ የትግሉን ሂደት እያስረዳ ባደባባይ በግልፅ ትግሉን ያካሂዳል። አንድ ማዕከል፣ አንድ ትግል! አንድ ሕዝብ! አንድ ሀገር! ይህ ነው የኢትዮጵያ ሕዝብ የጠየቀው። አንድ ኢትዮጵያዊ መንግሥት ለማቋቋም። ይህ የኢትዮጵያዊያን የነፃነት ንቅናቄ፤ ትግሉ የሚጠይቀውን መስዋዕትነት እየከፈለ፤ የትግሉ ሂደት ግፊት በሚፈጥረው የሽክርክሪት ዕድገት መሠረት፤ ወደፊት ይገፋል። ስለዚህ ማስተባበሩ፣ መተባበሩ፣ እና መጥራትና መጠራቱ የኛ የያንዳንዳችን ኢትዮጵያዊያን ግዴታ ነው። ኢትዮጵያዊነታችን አሁን ተጠይቋል። መልስ እንሥጥ! እኔ በeske.meche@yahoo.comእገኛለሁ።

ኢትዮጵያዊያን እንቆጠር!

eskemeche

የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ተቃውሞ እንደቀጠለ ነው

0
0

 የሸክ ኑሩ ግድያ ሴራ ነው
• ኢህአዴግ በሉዓላዊነት ላይ ያለውን ፖሊሲ ተቃውመዋል
• ‹‹አማኞችን በአሸባሪነት መክሰስ ትውልዱን ለመግደል የተደረገ የኢህአዴግ ሴራ ነው፡፡››
• ህወሓት ከስሯል
• የአንዳርጋቸው ጽጌ ጉዳይ
• አዲሲቷ ኢትዮጵያ የትኛዋ ናት?

ነገረ ኢትዮጵያ ባህርዳር፣ መቀሌ፣ ጎንደር፣ ደብረማርቆስ፣ ደሴ፣ ወልደያ፣ ደብረታቦርና ሌሎችም የሚገኙ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎችን ባገኘችው መረጃ መሰረት የተነሱትን ዋና ዋና ተቃውሞወች እንደሚከተለው አቅርባለች፡፡

SONY DSCአርሶ አደሩ አሁንም ድረስ ኢህአዴግ እየተደረገ ያለው የመሬት ድልደላ የፓርቲው አባል አይደሉም የሚባሉት አርሶ አደሮችን መሬት አልባ በማድረግ ለደጋፊዎቹ እየሰጠ መሆኑን በውይይቱ ወቅት ተገልጾአል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ በ1997 ዓ.ም ምርጫ ቅንጅትን መርጣችኋል እየተባሉ አሁንም ድረስ ጫና እየደረሰባቸው እንደሚገኝና፣ ይህም ለምርጫው ዝግጅት እንዳይሆን ተማሪዎቹ ስጋታቸውን ገልጸዋል፡፡

የእምነት ነጻነት በርካታ ኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች ለሶስት አመታት ሰላማዊ በሆነ መንገድ ድምጻቸው እንዲሰማ ቢጥሩም መንግስት እየወሰደው ያለው አፈና አግባብ አለመሆኑን፣ በተለይም በርካታ ቁጥር ያለውን ሙስሊሙን ማህበረሰብ በጅምላ አሸባሪ ብሎ መፈረጅ ስህተት መሆኑን በተማሪዎቹ ተነስቷል፡፡ በተመሳሳይ ‹‹ኢህአዴግ ማህበረ ቅዱሳንን አሸባሪ የሚልበት ምክንያት ምንድን ነው?›› የሚል ጥያቄ የተነሳ ሲሆን የግቢ ጉባዔ የማህበረ ቅዱሳን አንድ ክንፍ ነው ተብሎ በመፈረጁ አዲስ ህግ ወጥቶ ዩኒቨርሰቲ ውስጥ በጾም ወቅት ይሰጠን የነበረው አገልግሎትን ጨምሮ እምነታችን እንዳንተገብር መከልከላችን ለጣልቃ ገብነቱ ማሳያ ምክንያት ነው›› ብለዋል፡፡

ይህም መንግስት ከመቼውም ጊዜ በበለጠ በእምነት ላይ ጣልቃ እየገባ መሆኑን በውይይቱ ላይ ተነስቷል፡፡ እንደ ምሳሌም በ1989ና 1994 ዓ.ም የኃይማኖት አባቶች በተለይም ቄሶች የጦር መሳሪያ ደብቃችኋል ተብለው ድብደባ እንደደረሰባቸው በመግለጽ የጣልቃገብነቱን አስከፊነት ገልጸዋል፡፡ ሉዓላዊነት ሉዓላዊነትን በተመለከተ በበርካታ ዩኒቨርሲቲዎች ጥያቄ የተነሳ ሲሆን በተለይም በባህርዳር፣ ጎንደር፣ ወልደያ፣ ደሴና ደብረማርቆስ ዪኒቨርሲቲዎች ዋነኛ የመወያያ አጀንዳ እንደነበር ለመረዳት ችለናል፡፡ ተማሪዎቹ ‹‹መሬቱን ቆርሶ የሰጠው ኢህአዴግ ነው፣ በሉዓላዊነት ጉዳይ ላይ አገራችን ከነበራት ክብር እያሳነሰው ነው፣ ኢትዮጵያ አንድነትን ለመጠበቅ የጣረውን ምኒልክን እየወቀሰ ኢህአዴግ በአሁኑ ወቅት መሬት ቆርሶ መስጠቱ አላማውን በግልጽ የሚያሳይ ነው›› በማለት በሉዓላዊነት ላይ የተሳሳተ ፖሊሲ እንዳለው ተከራክረዋል፡፡

በተጨማሪም ‹‹ኤርትራ ተገንጥላለች፣ አሰብን አጥነተናል፣ ባድመ ላይ ወጣቱ አልቆ መሬቱን አሳልፎ ሰጥቷል፣ አሁን ደግሞ የመተማን መሬት አሳልፎ ለመስጠት በድብቅ መፈራረሙ በሉዓላዊነታችን ላይ ያለውን አሉታዊ አቋም የሚያሳይ ነው፡፡›› በሚል በሉዓላዊነት ላይ ያለውን የተሳሳተ ፖሊሲ ተቃውመዋል፡፡ በተመሳሳይ ተማሪዎቹ አያሌው ጎበዜ የፕሬዝዳንትነት ስልጣኑን ሳይጨርስ የወረደው መሬቱን ፈርሜ አልሰጥም ስላለ ነው፡፡›› ያሉት ተማሪዎቹ ለጥያቄዎቻቸው መልስ እንደሚፈልጉ ገልጸዋል፡፡ የሸህ ኑሩ ግድያ ደሴ ላይ የተማሪው ትልቅ መወያያ ከሆኑት ጉዳዮች መካከል የሸህ ኑሩ ግድያ በቀዳሚነት እንደሚገኝ የነገረ ኢትዮጵያ ምንጮች ገልጸዋል፡፡

slide-15ከተወያዮቹ መካከል ‹‹የሸክ ኑሩ ገዳይ የኢህአዴግ ደህንነቶች ናቸው፡፡ ይህም የተደረገው ኢህአዴግ በሙስሊሙ መካከል ልዩነት ለመፍጠርና እርምጃም ለመውሰድ እንዲመቸው የወሰደው ነው፡፡›› ማለታቸውን ለማወቅ ተችሏል፡፡ አንዳርጋቸው ጽጌ ደብረማርቆስ በሚገኙ ተወያዮች አጀንዳ ከነበሩት ጉዳዮች መካከል የአንዳርጋቸው ጽጌ ጉዳይ ይገኝበታል፡፡ ተማሪዎቹ ‹‹የመን አንዳርጋቸውን አሳልፋ መስጠቷ ትክክል አይደለም፣ የአንዳርጋቸው ጉዳይ ሽብርን መዋጋት ነው ወይንስ የፖለቲካ ባላንጣነት? የእንግሊዝ ዜጋ የሆነውንና እንግሊዝ በአሸባሪነት ያልፈረጀችውን ሰው አሸባሪ ማለቱ ጸረ ሽብር ህጉ ከእንግሊዝ ተመሳሳይ ህግ ጋር በምን ቢለያይ ነው? በጸረ ሽብር ኢህአዴግ ከእንግሊዝ በልጦ ነው ወይ? አሁን ያለበት ሁኔታም ለህዝብ ይፋ ሊሆን ይገባል የመሳሰሉ ጥያቄዎች ተነስተዋል፡፡ ማፈናቀል የከተማ ነዋሪዎችን ማፈናቀል በባህርዳር፣ ጎንደርና ደብረማርቆስ ከተማ ውስጥ የሚገኙት የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ተነስቷል፡፡

ተማሪዎቹ ‹‹በተለያዩ ከተሞች ድሃዎችን በማፈናቀልና ቤታቸውን በማፍረስ ለሀብታም እየተሰጠ ነው፡፡ ይህ የጭቆና የመጨረሻው ደረጃ ነው፡፡›› ሲሉ ተከራክረዋል፡፡ ‹‹የመሬት መቀራመት መሬት በቀብሬ ላይ ይቀየራል ከሚለው የኢህአዴግ ፖሊሲ የመነጨ ነው፡፡ የመሬት ክፍፍሉ አርሶ አደሩን ያገለለና ለስርዓቱ መጠቀሚያ የሆነ ነው፡፡ የሊዝ ህጉ መሰረዝ ይገባዋል፣ አርሶ አደሩ ከመሬት እየተነቀለ ነው፣ 1ለ5 አርሶ አደሩን ለማፈን የተደረገ ነው፡፡ መሬት የኢትዮጵያ ህዝብ እንጅ የመንግስትና የፓርቲ መሆን የለበትም›› የሚሉ ተቃውሞዎች ተነስተዋል፡፡ የባህር ዳሩ ግጭት የመላው ኢትዮጵያ ጨዋታዎች ላይ የተፈጠረው ግጭትን በተመለከተ ደሴ፣ ደብረታቦር፣ ባህርዳርና ጎንደር ላይ መወያያ ሆኖ እንደነበር ለማወቅ ተችሏል፡፡

ባህርዳር ላይ በተደረገው የመላው ኢትዮጵያ ጨዋታዎች ላይ የተፈጠረው ግጭት ብአዴን በበላይነት የመራው ሴራ መሆኑን፣ ይህም አማርኛ ተናጋሪውን እንደማይወክል፣ የብአዴን ፖለቲከኞች እንወክለዋለን የሚሉትን ህዝብ በአደባባይ ሲሳደቡ መስተዋላቸው የሚያሳየው ለህዝብ ያልቆሙ እንደሆነ ተማሪዎቹ አጽንኦት ሰጥተው እንደገለጹ ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡ ርዕዮት-ዓለም በተለይ ባህረዳር ውስጥ ድባንቄ የተባለ ቦታ ላይ የሚገኙት የባህርዳር ዩኒቨርሲቲ ሰልጣኞች በርዕዮት ዓለም ላይ ሰፋ ያለ ውይይት ማድረጋቸውን ለማወቅ ተችሏል፡፡ ‹‹እስከ 1994 ዓ.ም ኢህአዴግ ፖሊሲ አልነበረውም፣ ተቃዋዎችን ፖሊሲ የላቸውም እያለ ለመተቼት ምን ሞራል አለው፣ ሌብራሊዝም ተቃዋሚዎቹ ስለሚከተሉት ብቻ ትክክል እንዳልሆነ እየተነገረን ነው፣ ከቻይና ተገለበጠ የሚባል ርዕዮት ዓለም ለኢትዮጵያ እየጠቀመ አይደለም፣ መነሻውና መድረሻው የማይታወቅ የኢህአዴግ ርዕዮት ዓለም ኢትዮጵያ ውስጥ ለውጥ ሊያመጣ አልቻለም፣ ማህበረቅዱሳንንና ሙስሊሙን ማህበረሰብ አሸባሪ ማለት እምነት አልባ ትውልድ ለመፍጠር የተደረገ ሴራ ነው፣ ይህ ትውልዱን ለመግደል የተደረገ የኢህአዴግ ሴራ ነው፡፡››

ትምህርት ‹‹ትምህርትን በኢህአዴግ ዘመን ወድቋል፡፡ ትምህርቱ ጥራት ቢኖረው ኖሮ ተመርቆ ስራ አያጣም ነበር፡፡ አሁንም ስራ እንይዛለን የሚል ተስፋ የለንም፡፡ ኢህአዴግ ዘመን ትምህርት ወድቆ ትምህርት ስርዓቱን የጀመሩትን ስርዓቶች የማውገዝ ሞራል አላችሁ ሆይ?›› የሚሉ ተቃውሞዎች ቀርበዋል፡፡ በተጨማሪም ‹‹በየ ዩኒቨርሲቲው የሚገኙ ሴቶች በትምህርት ስርዓቱ ውድቀትና በድህነት ምክንያት ገላቸውን እየሸጡ ነው፡፡ ኢህአዴግ በግብረ ሰዶማውያን ላይ ያለው አቋም የተሳሳተ ነው፡፡ ይህም የሚደረገው ትውልዱ ማንነቱን ትቶ ውድቀት ላይ እንዲወድቅ ለማድረግ ነው፡፡ ሌሎች ጉዳዮች ላይ ሌብራሊዝምን እያንቋሸሸ የወሲብ ሌብራሊዝምን ግፍ ከሚገባው በላይ ለቆታል፡፡ ይህ ኢህአዴግ ስልጣኑን ለማቆየት የሚያደርገው ስልት ነው፡፡ ይህ በተሳሳተ የኢኮኖሚ ምክንያት በመጣው ድህነት የተነሳ ነው፡፡ በትምህርት ውድቀትና በድህነቱ ምክንያት ተማሪዎች ድንጋይ መቀጥቀጥ አማራጭ ሆኖ በመቅረቡ ሴቶች የወሲብ ንግድን እንዲቀላቀሉ እንዲሁም ወንዶች የጎዳና ተዳዳሪ እንዲሆኑ እየተደረገ ነው፡፡ የሚሉ ተቃውሞዎችን ማቅረባቸውን ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡›› የሚሉ ተቃውሞዎች ተነስተዋል፡፡

ኢዲሲቷ ኢትዮጵያ የትኛዋ ናት? ለስልጠና በቀረቡት ሰነዶች አብዛኛዎቹ ክፍሎች ውስጥ ‹‹አዲሲቷ ኢትዮጵያ›› የሚል ቃል የተደጋገመ ሲሆን ተማሪዎቹም ‹‹ኢዲሲቷ ኢትዮጵያ የትኛዋ ናት? ኤርትራ የተገነጠለችባት፣ በቋንቋ የተከፋፈልንባት፣ ወደብ አልባ የሆንንባት፣ የኢትዮጵያ ገናናነት የወረደባት ኢትዮጵያ አዲሲቱ ኢትዮጵያ ልትባል ትችላለች? የሚሉ ጥያቄዎችን አንስተዋል፡፡ በተጨማሪም ‹‹ብሄር ማለት ምን ማለት ነው?›› የሚለው ወልደያ፣ ባህርዳር፣ ጎንደር፣ ደብረማርቆስ በሚገኙ ሰልጣኞች ሰፊ ክርክር አስነስቷል፡፡ ፋብሪካዎች ደብረማርቆስ የሚገኙ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ‹‹ደብረ ማርቆስ ውስጥ ሊገነባ የነበረ የመኪና መገጣጠሚያ እንደገና እንዲቀር ተደርጓል፣ በክልሉ የቢራ እንጅ ሌሎች ፋብሪካዎች እንዲስፋፉ አይደረግም›› የሚል ጥያቄ አንስተዋል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ ‹‹በስፋት ደን ይመነጠራል፡፡ ደን እየተመነጠረ እንዴት አረንጓዴ ልማት አለ ይባላል?›› የሚሉ ጥያቄዎችን ተጠይቀዋል፡፡

ህወሓት ከስሯል
በመቀሌ ዪኒቨርሲቲ የሚገኙ ሰልጣኝ ተማሪዎች በተለይም በህወሓት ላይ ጥያቄ ማንሳታቸውን ስማቸው እንዲገለጽ ያልፈለጉ አሰልጣኝ ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡ ተማሪዎቹ ‹‹የትግራይ ህዝብ በህወሓት አምኖና ከሌላው ህዝብ ተለይቶ እንዲኖር ህወሓት ብዙ ስራ ሰርቶ ነበር፡፡ ከክፍፍሉ በኋላ ግን ህወሓት ከስሯል፡፡ የትግራይ ህዝብን ጥያቄ ያልተመለሰ ለመሆኑ የአረና መፈጠር አንድ ማሳያ ነው፡፡›› ማለታቸውን አሰልጣኙ ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡ በተጨማሪም አብርሃ ደስታ ላይ የተወሰደው እርምጃም መነጋገሪያ እንደሆነም ለማወቅ ችለናል፡፡ ተማሪዎቹ አብርሃ ደስታ መፈታት እንዳበት መጠየቃቸውንም ለማወቅ ተችሏል፡፡ በሌላ በኩል በአብዛኛዎቹ ዩኒቨርሲቲዎች ጥያቄውን ያነሱት ተማሪዎች በቡድን ውይይት ወቅት ማስፈራሪያ እየደረሰባቸው እንደሆነም ተገልጾአል፡፡ በጅማ፣ አዳ፣ ሀዋሳና ሌሎች ከተሞች የሚሰለጥኑ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ያሰሙትን ተቃውሞና መከራከሪያዎች በቀጣይነት ለማቅረብ እንሞክራለን፡፡

Minilik Salsawi (ምንሊክ ሳልሳዊ)

 

ዝም ብለህ አትፍረድ!

0
0

ከጌታቸው ሽፈራው

ባለፈው ሶስትና አራት ወር ውስጥ ብቻ 17 ያህል ጋዜጠኞች አገር ጥለው ተሰድደዋል፡፡ በተለይ ባለፈው ሳምንት 12 ያህል ጋዜጠኞች ሲሰደዱ በርካታ ኢትዮጵያውያን ‹‹ለምን ተሰደዱ?›› የሚለውን በደንብ ሳያጤኑ ለመውቀስ ሲጥሩ ተመልክቻለሁ፡፡ በእርግጥ ጋዜጠኞቹ መሰደዳቸውን አልደግፍም፡፡ ነገር ግን እነዚህ ጋዜጠኞች ለምን ተሰደዱ ብለን ሳናጤን መውቀስም ተገቢ መስሎ ስላልታየኝ ነው፡፡

ከተሰደዱት መካከል ሁለቱን ብቻ ልጥቀስ፡፡ ተሰማ ደሳለኝ ይባላል፡፡ ኢቦኒ የተሰኘች መጽሄት ነበረችው፡፡ ተሰማ ፌስ ቡክና ኢንተርኔት ለቅሞ ከማሳተም ይልቅ ጋዜጠኛ ቀጥሮ ያሰራ ነበር፡፡ መጽሄቷ የሙያውን ስነ ምግባር የጠበቀች እንድትሆንም ጥሯል፡፡ ነገር ግን የመንግስት ስውር እጆች በሚቃኙት ማከፋፈያ (በተለይም ሁለተኛ ደረጃ አከፋፋዮች)፣ የህትመት ዋጋ አንዱ ፈተና ነበር፡፡ ተሰማ ስፖርትና ፋሽን ላይ የሚሰሩ መጽሔቶች ማስታወቂያ እንደሚያገኙ፣ የመንግስት ጫና እንደማይደርስባቸው ያውቃል፡፡ እሱ ግን የመረጠው ለአገሬ ህዝብ ይጠቅማል ያለውን ፖለቲካዊ፣ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮችን ማንሳት ነው፡፡ በእነዚህ ጉዳዮች የሚያጠነጥኑት ደግሞ ማስታወቂያ አያገኙም፡፡ ይታፈናሉ፣ ማተሚያ ቤት አያገኙም፡፡ እናም ኢቦኒ ገበያውን መቋቋም አልቻለችም፡፡ እንዲያውም እዳ አለብህ ተባለ፡፡ ተሰማ ልጅና ቤተሰብ አለው፡፡ ተቋሙ ግን ተዘግቷል፡፡ እንዲህም ሆኖ እዳውን ካልከፈለ የሚጠብቀው እስራት ነው፡፡ አሊያም ጎዳና፡፡ በዚህን ወቅት አንድም ሰው ሊያግዘው አልቻለም፡፡ በህትመት ላይ እያለም ለዴሞክራሲያዊ ግንባታ በሚያደርገው አስተዋጽኦ ይህ ነው የሚባል ማስታወቂያ አያገኝም ነበር፡፡ እናም ለአገሩ ሰርቶ መኖር ብቻ ሳይሆን በአገሩ ሰርቶ መኖር ሲያቅተው ከሁለት ወር በፊት አገሩን ጥሎ ተሰደደ፡፡

Lomi-magazine-ሌላኛው አስናቀ ልባዊ ነው፡፡ አስናቀ የጃኖ መጽሄት ባለቤት ነው፡፡ መጻፍ አደገኛ መሆኑን እያወቀም ቢሆን ሲጽፍ ቆይቷል፡፡ ስርዓቱ የማይፈልጋቸውን ጉዳዮች ላይ ዜናዎችን ሲሰራ ‹‹አለቀለት!›› ተብሏል፡፡ ይህን ስራ በድፍረት እየሰራን ቢሆን መሰረታዊ የሆነ የሚዲያው ችግሮች እሱንም አልለቀቁትም፡፡ ማስታወቂያ ማግኘት እጅጉን ፈታኝ ነው፡፡ ከዚህ አለፍ ሲል ደግሞ ተከሰሰ፡፡ በትንሹ 50 ሺህ ብር ቢቀጣ የት አምጥቶ ይከፍላል? እሱም ለአገሩ ሰርቶ መኖር ይቅልና ሰርቶ መኖርም ፈታኝ ሆነብኝ ብሎ ተሰደደ፡፡

የኢትዮ ምህዳሩ ኤፍሬም ያ በደል የደረሰበት ሲሰርቅ ተይዞ አይደለም፡፡ እስክንድር፣ ርዕዮትና ውብሸት የታሰሩት ሲጽፉ ነው፡፡ በጣም የሚያሳዝነው 90 ሚሊዮን ህዝብ ባላት ኢትዮጵያ 80ና 90 ሺህ ብር ለማውጣት አልተቻለም ነበር፡፡ ውብሸት ታየን በትንሹም ቢሆን ያስታወስነው ፈረንጆቹ ከሸለሙት በኋላ ነው፡፡ የዚህ ትንታግ ጋዜጠኛ ልጅ ትምህርቱን ለማቋረጥ ምንም አልቀረውም ነበር፡፡ ሚስቱ ብዙ ተቸግራለች፡፡ እስክንድር ነጋን የምንጠይቀው ስንቶቻችን ነን? እጅግ በጣም ጥቂቶቹ! ጋዜጠኛ ሲሰደድ ግን አብዛኛው ኢትዮጵያዊ ወቀሳችንን እናዥጎደጉዳለን፡፡ አስናቀና ተሰማ ኤፍሬም ተጎድቶ አብዛኛው ባለሃብት፣ ዲያፖራ፣ ምሁር……ፀጥ ሲል የአይን እማኞች ነበሩ፡፡ የውብሸት ታዬ ልጅና ሚስት መቸገራቸውንና እሱም አስታዋሽ ማጣቱን ከእነሱ በላይ የታዘበ የለም፡፡ ወደድንም ጠላንም ጋዜጠኛም ሰው ነውና አለኝታ ይፈልጋል፡፡ ይህን ሲያጣ ደግሞ ስደትን ሊመርጥ ይችላል፡፡

እነዚህ ሚዲያዎች እየሰሩ በነበረበት ወቅት ማስታወቂያ ሲጠይቋችሁ ‹‹አይ ፖለቲካ ነው የምትጽፈው!›› ብላችሁ ፊታችሁን ያላጠቆራችሁ (ካላችሁ)፣ ስህተት ስታዩበት እንዲሻሻል ደውላችሁ የጠየቃችሁ፣ አንድም መረጃ አገኝበታላሁ ብላችሁ፣ አሊያም በመግዛታችሁ ሚዲያው ይጠናከራል ብላችሁ የገዛችሁ ‹‹ጥለውን ሄዱ!›› ብላችሁ ብታማርሩ ምክንያት ይኖራችኋል፡፡ ይገባችኋልም!

ነገር ግን ለስፖርትና ፋሽን ማስታወቂያ እየሰጠህ እነዚህ መጽሄቶች ማስታወቂያ ሲጠይቁ ‹‹ፖለቲካ ነው የምታሳትሙት!›› ብለህ መልሰህ አሁን ሲሰደዱ ‹‹አይ የእኛ አገር ጋዜጠኞች!›› ያልክ ነጋዴ ለመፍረድ ሞራል የለህምና አትፍረድ! ቃለ መጠይቅ ለማድረግ ሲደወልልህ ‹‹አይ ይህ መንግስት እኮ…ቅብጥርጥስ›› ብለህ የሸሸህ ‹‹ምሁር›› ጋዜጠኞቹ ተሰደዱ ብለህ እንዳትፈርድ፣ አንተም ድሮም የኢትዮጵያውያን ጉዳይ አያገባኝም ብለሃል አሁን እንዳትፈርድ! ያኔ እነዚህ መጽሄቶችን እንዲሁ አይተህ ያለፍክ ‹‹አንባቢ›› አታውቃቸውምና ተሰደዱ ብለህ እርር ድብን እንዳትል፣ እንዳትፈርድ!

እነዚህ ጋዜጦች አትምልን ሲሉህ ‹‹መንግስት በተዘዋዋሪም ሆነ በቀጥታ ጫና ያደርስብኛል፣ ለምን ስፖርት አታሳትምም….›› ያልክ የማተሚያ ቤት ባለቤት አሁን ጋዜጠኞች ተሰደዱ ብለህ ከመፍረድህ በፊት የአንተን አስተዋጽኦም መርምር! ኢትዮጵያ ውስጥ ሚዲያዎች በእሳት ላይ መቀመጣቸውን እያወክ፣ ማገዝም እየቻልክ ሲሰደዱ ብቻ በመቆዘም፣ ሲታሰሩ የፌስ ቡክ ፎቶውን በመቀየር ብቻ ለውጥ የሚመጣ የሚመስለህ ዳያስፖራ ‹‹አይ ጋዜጠኛ!›› ከማለት በፊት ‹‹እኔ ምን አደረኩ?›› ብለህ መጠየቅ ይገባሃል፡፡
Lomi-magazine-
የኢትዮጵያውያንን መብት ለማስጠበቅ ተቋቁሞ ጋዜጠኞች ሲታሰሩ፣ ሚዲያዎች ሲዘጉ ሀሳብን በነጻነት ለመግለጽ ነጻነት ያልጮህክ ተቃዋሚና ፖለቲከኛ አሁን ሲወጡ ‹‹አቤት ፍርሃት!›› ከማለት በፊት የራሰህን አስተዋጽኦ መገምገም የግድ ነው፡፡ ለሚዲያውም ሆነ መረጃ አገኝበታለሁ ብለህ ሚዲያዎቹን በመግዛት የራስህን አስተዋጽኦ ያላደረክ ‹‹አንባቢ›› በስሚ ስሚ ‹‹ተሰደዱ!›› አደራህን እብዳትፈርድ!

የትም ሁኑ የት፣ እናንተ! የጋዜጠኞችን መብት ይከበር ዘንድ ያለ ፍርሃት በድፍረት የጮኻችሁ ‹‹ለምን ተሰደዱ?›› ብላችሁ ብትወቅሱ ምክንያት ይኖራችኋል፡፡ ማስታወቂያ ሲጠይቋችሁ የሰጣችሁ፣ አንብባችሁ ገንቢ አስተያየት የለገሳችሁ፣ ያበረታታችሁ ብቻ በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ጋዜጠኞች ለሚዲያ፣ ሚዲያው ለዴሞክራሲ፣ ዴሞክራሲው ለኢትዮጵያውያን ይጠቅማል ብላችሁ ይብዛም ይነስም የራሳችሁን አስተዋጽኦ ያደረጋችሁ ‹‹ለምን ተሰደዱ?›› ብትሉ ያምርባችኋል! ያገባናል ብላችሁ የቻላችሁትን ሁሉ አድርጋችኋልና!


ከሰሞኑ የተሰደዱት 7 ጋዜጠኞች – (ፎቶዎች)

0
0

gezetegna

gezetegna 3

gezetegna 1

daniel dirsha

asnake

ጋዜጠኛ ቶማስ አያሌው

ጋዜጠኛ ቶማስ አያሌው

ጋዜጠኛ ግዛው ታዬ

ጋዜጠኛ ግዛው ታዬ


የኢህአዴግ መንግስት በጋዜጠኞች ላይ የሚያደርሰውን ጫና ተከትሎ ከሀገር የተሰደዱትን የሎሚ፣ ጃኖ እና አፍሮ ታይምስ ጋዜጠኞችን ፎቶ ከዚህ እንደሚከተለው ይዘን ቀርበናል፡፡
1.ጋዜጠኛ ግዛው ታዬ የሎሚ መጽሔት ማኔጂንግ ዳይሬክተር
2. ጋዜጠኛ ቶማስ አያሌው የአፍሮ ታይምስ ማኔጂንግ ዳይሬክተር
3. ጋዜጠኛ ዳንኤል ድርሻ የሎሚ መጽሔት ሚዲያ ዳይሬክተር
4. ጋዜጠኛ ሰናይ አባተ የሎሚ መጽሔት ዋና አዘጋጅ
5. ጋዜጠኛ ሰብለወርቅ መከተ የሎሚ መጽሔት ከፍተኛ ሪፖርተር
6. ጋዜጠኛ አቦነሽ አበራ የሎሚ መጽሔት ከፍተኛ ሪፖርተር
7.ጋዜጠኛ አስናቀ ልባዊ የጃኖ መጽሔት ማኔጂንግ ዳይሬክተር

የብሔራዊ እርቅና መግባባት ጉዳይ (ዶ/ር ዘለዓለም እሸቴ ይመር)

0
0

reconsiliationስለ ብሔራዊ እርቅና መግባባት ጉዳይ አጠር ምጥን ተደርጎ የተዘጋጀውን ባለ አምስት ነጥብ የዳሰሳ ጥናት (survey) ለዚሁ ጉዳይ ሲባል ብቻ ወደ ተዘጋጀው ድህረ ገፅ  www.MyEthiopia.com በመሄድ ድምፅዎን ያሰሙ። የዝምተኛው ብዙሃን ድምፅ ጭምር ሳይቀር እስቲ ይሰማ! ፖለቲካውንና ፍልስፍናውን አርባ አመት አውጠንጥነን አረጀንበት። እንዲሁ ስንባዝን እድሜያችን አልቆ አንድ ባንድ ወደ ሞት ልንሄድ ነው። እርቅና መግባባትን ማን ጠላ? መላው ጠፍቶብን እንጂ። አይ መላውም አልጠፋን እንደ እውነቱ ከሆነ። ኢትዮጵያ መፍትሔ ሊያመጡ የማይሳናቸውን ልጆች ወልዳ ሳለ እንደ መካን ቁጭ ብላ መቆዘም አይገባትም። እስቲ የልበ ሰፊው፦ የአስተዋዩና የጨዋው ሕዝብ ድምፅ እንስማው። - ––[ሙሉውን ለማንበብ እዚህ ይጫኑ]

በቅርስነት የተመዘገበ ሕንፃ በልማት ምክንያት እንዲፈርስ መታዘዙ ተቃውሞ አስነሳ

0
0

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በልደታ ክፍለ ከተማ ውስጥ የሚገኘውንና በቅርስነት የተመዘገበውን ታዋቂው ሎምባርዲያ ሬስቶራንት ያለበትን ሕንፃ ጨምሮ፣ በ10.6 ሔክታር ላይ የሚገኙ ግንባታዎችን ለማፍረስ ለተነሺዎች የመጨረሻ

ማስጠንቀቂያ ሰጠ፡፡ የመጨረሻ ማስጠንቀቂያው ባለፈው ዓርብ አብቅቷል፡፡ በተለይ የሕንፃው ባለቤት የሆነው የመንግሥት ቤቶች ኤጀንሲና የሕንፃው ተከራዮች የአስተዳደሩን ውሳኔ ተቃውመዋል፡፡ 

ተቃውሞ አቅራቢዎቹ ሕንፃው በቅርስነት የተመዘገበ ሆኖ ሳለ እንዲፈርስ መወሰኑ አግባብ አይደለም እያሉ ነው፡፡ 

9f29a3148b9e3fb75491b584002f31bd_Lሕንፃው በ1921 ዓ.ም. የተገነባ ሲሆን፣ ሕንፃውን የገነቡት የመናዊው ታዋቂ ነጋዴ ሼክ አህመድ ሳላህ አልዛህሪ ናቸው፡፡ ሕንፃው ከ85 ዓመታት በላይ ከማስቆጠሩም በተጨማሪ የሥነ ሕንፃ ቦርድ በቅርስነት አስመዝግቦታል፡፡ 

የአዲስ አበባና ዙሪያዋ ኦሮሚያ ልዩ ዞን የተቀናጀ የጋራ ፕላን ፕሮጀክት ጽሕፈት ቤት ለአዲስ አበባ ከተማ ፕላን ኢንስቲትዩት በጻፈው ደብዳቤ፣ በተመሳሳይ በልደታ ክፍለ ከተማ የሚገኘው የሼክ አህመድ ሳላህ ቤት በአዲሱ ማስተር ፕላን ላይ በቅርስነት እንዲመዘገብ መደረጉን አስታውቋል፡፡ 

ከዚህ በተጨማሪም የከተማ ፕላን ኢንስቲትዩት፣ የባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር፣ የአዲስ አበባ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ ሕንፃው በቅርስነት ስለመያዙ፣ እንዲሁም የሚመለከተው አካል ለቅርሱ ጥበቃ እንዲያደርግ አሳስበዋል፡፡ 

ነገር ግን የልደታ ክፍለ ከተማ፣ የከተማ ማደስና መሬት ባንክ ጽሕፈት ቤት ለዚህ ማሳሰቢያ ትኩረት እንዳልሰጠ ታውቋል፡፡ 

የጽሕፈት ቤቱ ኃላፊ አቶ ለምለም ገብረ ሚካኤል ለሪፖርተር እንደገለጹት፣ ሕንፃው ቅርስ መባሉ አያሳምንም፡፡ ይልቁኑም በአካባቢው በሚካሄደው መልሶ ማልማት ከ40 እና ከ50 ፎቅ በላይ ከፍታ ያላቸው ሕንፃዎች ስለሚገነቡ መፍረሱ አግባብ እንደሆነ ተከራክረዋል፡፡ ‹‹እነዚህ ግንባታዎች በማዕከላዊው የከተማው ክፍል ሰማይ ጠቀስ ሕንፃዎች እንዲገነቡ በተያዘው ዕቅድ መሠረት የሚካሄዱ ናቸው፤›› ሲሉም አቶ ለምለም ጨምረው ገልጸዋል፡፡ 

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በሚያካሂደው መልሶ ማልማት ከብዙ ቅርሶች መፍረስ በኋላ፣ ልማቱ ቅርሶችን ታሳቢ ባደረገ መንገድ እንዲከናወን በቅርቡ መመርያ ማስተላለፉ ተገልጿል፡፡ ነገር ግን አሁንም የሚካሄዱ ልማቶች መንግሥት በቅርስነት ላስመዘገባቸው ግንባታዎች ትኩረት ገና አልሰጠም ሲሉ በርካታ ባለሙያዎች ይተቻሉ፡፡ 

የሕንፃው ባለቤት የነበሩት ሼክ አህመድ ሳላ አልዛህሪ በደቡብ የመን ረዳአ በተባለ ቦታ በ1873 ዓ.ም. ነው የተወለዱት፡፡ የአዲስ አበባ ፕሬስ በ1998 ዓ.ም. ባሳታመው የፊታውራሪ ተክለ ሃይማኖት ተክለ ማርያም ግለ ታሪክ፣ እንዲሁም ‹‹ከእንጦጦ ሐሙስ ገበያ እስከ መርካቶ›› በተሰኘ መጽሐፍ ላይ የሼክ አህመድ የሕይወት ታሪክ ተጽፏል፡፡ 

በመጽሐፉ እንደተገለጸው ሼክ አህመድ ታዋቂ ነጋዴ ከመሆናቸው በተጨማሪ፣ ለኢትዮጵያ ገቢና ወጪ ዕቃዎች የጉምሩክ አስተላላፊነት ኃላፊነት ተሰጥቷቸው ያስተዳድሩ ነበር፡፡ ከዚህ በተጨማሪ ፋሺስት ጣሊያን ኢትዮጵያን በወረረበት ጊዜ ለኢትዮጵያውያን አርበኞች ደጀን ነበሩ፡፡ 

ሕንፃው ሁለት ፎቅ ከፍታ ሲኖረው፣ ቀደም ሲል በሆስቴልነት ሲያገለግል ቆይቷል፡፡ በአሁኑ ወቅት ለመኖርያነት፣ ለንግድና ለቢሮ አገልግሎቶች ይሰጣል፡፡ 

Source:: Ethiopian Reporter

የአቶ ኤርሚያስ አመልጋ የመመለስ ጥያቄን መንግሥት እየመከረበት ነው

0
0

የአክሰስ ሪል ስቴትን ጉዳይ እንዲመለከት የመንግሥት ከፍተኛ ባለሥልጣናትና የሪል ስቴቱ ደንበኞች ተወካዮችን በአባልነት አቅፎ የተቋቋመው ዓብይ ኮሚቴ፣ ለመጀመርያ ጊዜ የተፈጠረውን ችግር ማየት ጀመረ፡፡

91a3c8437640a9ef1746719d4a2d53c4_Lየአክሰስ ሪል ስቴት መሥራችና ሊቀመንበር አቶ ኤርሚያስ አመልጋ ወደ አገር ለመመለስ ያቀረቡትን ጥያቄ እየመከረበት ነው፡፡

የሪፖርተር ምንጮች እንደገለጹት፣ የአክሰስ ሪል ስቴትን ጉዳይ እንዲመለከት የተዋቀረው ዓብይ ኮሚቴ የመጀመሪያውን ይፋ ስብሰባ ያደረገው ባለፈው ዓርብ ነሐሴ 16 ቀን 2006 ዓ.ም. ነበር፡፡

በንግድ ሚኒስቴር ተወካይ የሚመራው ዓብይ ኮሚቴ በመጀመሪያው ስብሰባው አቶ ኤርሚያስ አመልጋ ወደ አገር ተመልሰው ኩባንያውን እንደገና ለማስቀጠል አቅርበውታል በተባለው ተደጋጋሚ ጥያቄ ላይ መወያየቱ ታውቋል፡፡

አቶ ኤርሚያስ አክሰስ ሪል ስቴት የገጠመውን ችግር ለመፍታትና በአገር ውስጥ ሆነው ለመሥራት ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ጭምር በደብዳቤ ገልጸው እንደነበር የሚጠቁሙት ምንጮች፣ በአክሰስ ሪል ስቴት ዙሪያ ከዚህ በኋላ መወሰድ የሚኖርበት ዕርምጃ ምን መሆን እንዳለበት ውይይት ተደርጐበታል ብለዋል፡፡

በጉዳዩ ላይ በቀጥታ መንግሥት ጣልቃ በመግባት መፍትሔ ሊሆን የሚችለውን ዕርምጃ ለመውሰድ እንዲያስችል፣ ከተለያዩ መንግሥታዊ መሥሪያ ቤቶች አክሰስ ሪል ስቴትን የሚመለከቱ መረጃዎች ተጠናክረው ለኮሚቴው እንዲቀርቡ ተወስኗል፡፡

ለዓብይ ኮሚቴው ይቅረቡ የተባሉ መረጃዎችን በመያዝ መፍትሔ ይሆናል የተባለውን ውሳኔ እስከ ነሐሴ 30 ቀን 2006 ዓ.ም. ድረስ ለመወሰን ስምምነት ላይ መደረሱን ምንጮች ያስረዳሉ፡፡

አቶ ኤርሚያስ ወደ አገር ቤት ተመልሰው ችግሩን ለመፍታት እንደሚችሉ፣ ይህንንም ለማድረግ አስፈላጊውን ዝግጅት ማድረጋቸውንና ለዚህም ዋስትና እንዲሰጣቸው በደብዳቤ አቅርበዋል የተባለውን ጥያቄያቸውን ተከትሎ፣ ጉዳዩ የሚመለከታቸው አካላት ከአቶ ኤርሚያስ ጋር ንግግር ሳይጀምሩ እንዳልቀረ እየተነገረ ነው፡፡

ሆኖም አቶ ኤርሚያስ ወደ አገር ተመልሰው እንዲሠሩ የሚፈቀድ ከሆነ በሕግ አግባብ ያስኬዳል አያስኬድም የሚለውን ጉዳይ ይኼው ዓብይ ኮሚቴ እንደተነጋገረበትም ምንጮች ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡ በተለይም የአክሰስ ሪል ስቴት ተጐጂዎች ይህንን ሐሳብ እንዴት ይቀበሉታል የሚለውም ሌላው አነጋጋሪ ጉዳይ ነበር ተብሏል፡፡

ለዓብይ ኮሚቴው መዋቀር ዋና ምክንያት የአክሰስ ሪል ስቴት ደንበኞች ችግሩን በተመለከተ መንግሥት ጣልቃ ገብቶ መብታቸውን እንዲያስጠብቅላቸው ባቀረቡት ጥያቄ መሠረት ነው፡፡ መንግሥትም ጉዳዩን በማየት ዓብይ ኮሚቴው እንዲዋቀር ያደረገ ቢሆንም፣ ኮሚቴው ብዙም ሳይንቀሳቀስ በመቅረቱ በቤት አሠሪዎች ዘንድ ቅሬታ ፈጥሮ ቆይቷል፡፡

አሁን እየተደረገ ያለው እንቅስቃሴ ግን መንግሥትም ለጉዳዩ ትኩረት እየሰጠ መሆኑን የሚያሳይ እንደሆነ፣ ሊወሰድ የሚችለውን ውሳኔ ለመወሰን ግን ከባድ ሊሆን ይችላል የሚል ሥጋት አለ፡፡ በተለይ ከአክሰስ ሪል ስቴት ቤት አሠሪዎች በተጨማሪ አክሰስ ሪል ስቴት ላይ ገንዘብ አለን የሚሉ ወገኖች መኖራቸው ጉዳዩን ይበልጥ እንዳወሳሰበው ምንጮች አመልክተዋል፡፡

እስከ ነሐሴ 30 ቀን 2006 ዓ.ም. ዓብይ ኮሚቴው ይወስናል ተብሎ የሚጠበቀው ውሳኔ የአክሰስ ሪል ስቴትና የደንበኞቹ ዕጣ ፈንታ ምን ሊሆን እንደሚችል ያመላክታል ተብሎም እንደሚጠበቅ ተጠቁሟል፡፡

ጉዳዩን እንዲመለከቱ በዓብይ ኮሚቴ ውስጥ እንዲካተቱ የተደረጉት ንግድ ሚኒስቴር፣ የቤቶች፣ ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ሚኒስቴር፣ የፌዴራል ፖሊስ፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር፣ የፍትሕ ሚኒስቴር፣ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር፣ የሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ ጽሕፈት ቤት የሪል ስቴቱ ደንበኞች ተወካዮች ናቸው፡፡

ቁጥራቸው ከሁለት ሺሕ በላይ የሆኑ ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያዊያን አክሰስ ሪል ስቴት የመኖሪያ ቤት እንዲገነባላቸው ገንዘብ ከፍለው፣ በውሉ መሠረት ሳያስረክባቸው አቶ ኤርሚያስ ከአገር መውጣታቸው ይታወሳል፡፡ በወቅቱ አቶ ኤርሚያስ በርካታ ደረቅ ቼኮች እየፈረሙ ገንዘባቸው እንዲመለስላቸው ለሚፈልጉ ደንበኞች በመስጠታቸው ምክንያት፣ በተለይ በአንድ ግለሰብ ክስ ተመሥርቶባቸው ነበር፡፡

ተጎጂዎች በመሰባሰብ ለመንግሥት አቤት በማለታቸው መንግሥትም ሕጋዊና አስተዳደራዊ መፍትሔ ለመስጠት ጉዳያቸውን ከፍተኛ የመንግሥት ባለሥልጣናት የተካተቱበት ኮሚቴ በማዋቀር ጭምር ሲከታተለው እንደነበር መዘገባችን አይዘነጋም፡፡

Source:: Ethiopian Reporter

“በበዓሉ ግርማ ጉዳይ ላይ ከሕሊና ዕዳ ነጻ ነኝ”

0
0

ደራሲና ሐያሲ አስፋው ዳምጤ

ደራሲና ሐያሲ አስፋው ዳምጤ ናደው፣ የተወለዱት መጋቢት 1ዐ ቀን 1927 ዓ.ም. አዲስ አበባ ጊዮርጊስ አካባቢ፣ መርሐ ጥበብ
ማተሚያ ቤት ግቢ ከሚባለው ቦታ ነው፡፡
አቶ አስፋው የቤተ ክህነት ትምህርት ለጥቂት ጊዜ ከተማሩ በኋላ፣ በዘመናዊ ትምህርት፣ የመጀመሪያና ሁለተኛ ደረጃን፣ በኮከበ
ፅባሕ ቀ.ኃ.ሥ. አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት፣ በመጀመሪያ ዲግሪ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ፣ በሁለተኛ ዲግሪ ደግሞ
በእንግሊዙ ኪምብሪጅ ዩኒቨርሲቲ ተምረው ተመርቀዋል፡፡
ወደሥራ ዓለም ከተቀላቀሉ በኋላ፣አብዛኛውን የሥራ ጊዜያቸው በገንዘብ ሚኒስቴር በተለያዩ የኃላፊነት ደረጃዎች ያገለገሉ ሲሆን፣
ከገንዘብ ሚኒስቴር እንደለቀቁ በኢትዮጵያ መጽሐፍ ድርጅትና በኩራዝ አሳታሚ ሠርተዋል፡፡
አቶ አስፋው ከኢትዮጵያ ውጭ ካሳለፉት ሰባት ዓመታት ውስጥ፣ በእንግሊዝ ለትምህርት ሶስት ዓመት፣ ቀሪውን አራት ዓመት
ደግሞ በአሜሪካ በሥራ ነበር::
asfaw_damte
በድርሰቱ ዓለምም፣ “አንድ ለአምስት” የተሰኘ ረጅም ልቦለድ ያበረከቱ ሲሆን፣ በደራሲያን ማኀበር ካሳተመው በ“የዘመነ
ቀለማት” መፍሐፍ ላይ በአጫጭር ግጥሞቻቸው፣ በ‹‹እነሆ››መድብል ደግሞ በአጫጭር ታሪኮች ተሳትፈዋል፡፡ከዚህም
በተጨማሪ ከ1970 እስከ 90ዎቹ ዓመታት ድረስ ስለ አማርኛ ጥበበ ቃላት አንዳንድ ነጥቦችን ከስር ጀምረው መጣጥፎችን
አበርክተዋል፡፡

ደራሲና ሐያሲ አቶ አስፋው ዳምጤን የረጅም ጊዜ ጓደኛቸው ከነበረውና የደርግ ጅቦች ሰለባ ከሆነው ታዋቂውና ተወዳጁ ደራሲ
በዓሉ ግርማ ከሚወደው ሕዝብ ጋር የመጨረሻው በነበረችው ምሽት ከአቶ አስፋው ዳምቴ ጋር በሰላም አብረው ከተዝናኑ
በኋላ ፣ተሰነባብተው ሌላ ታሪክ እስኪፈጠር ድረስ፣በአንዲት ግሮሰሪ ደጅ ላይ አብረው አብረው ነበሩ፣
መጽሔታችንም “ማን ያርዳ የቀበረ፣ ማን ይናገር የቀበረ” እንደሚባለው፣ስለበዓሉ ግርማ የመጨረሻዋ ምሽት በዝርዝር
እንዲነግሩን አቶ አስፋው ዳምጤን ጋብዘናቸዋልና እነሆ::

ፍቱን፦- የደራሲ በዓሉ ግርማ ባለቤት፣ ወ/ሮ አልማዝ አበራ፣ ‹‹…የካቲት 24 ቀን 1976 ዓ.ም. ቀን ላይ አስፋው ዳምጤ
እቤት ስልክ ደወለ :: በዓሉ ቤት አልነበረምና፣ ስልኩን አንሥቼ ያነጋገርኩት እኔ ነበርኩ :: የእግዜር ሰላምታ ከተለዋወጥን
በኋላ፣ ‹… በዓሉ እንደመጣ እዚያ እቀጠሯችን ቦታ ባስቸኳይ እንድትመጣ ብሎሃል በዪልኝ …› ብሎ ስልኩን ዘጋ ::››
ብለዋል:: እውነት ነው ?
bealu-girma1
አቶ አስፋው፦ የዚህ አጭር መልሱ ‹ሐሰት ነው› ነው:: ይኸንኑ መልስ ለሚያዚያ 8 ቀን ውንጀላቸው፣ በሚያዝያ 15 ቀን
1989 እፎይታ ጋዜጣ ላይ ከዛሬ 16 ዓመት በፊት ሰጥቼያለሁ ::
በዚያው ወቅት ስለዚያች ዕለት የበዓሉ ከቤት አወጣጥ ፣ Black Lions (ብላክ ላየንስ) የተባለ፣ የበርካታ ኢትዮጳውያን
ደራስያንን የሕይወት ታሪክ እና ሥራዎ ቻቸውን ለማስተዋወቅ የሚጥር መጽሐፍ ደራሲ፣ ሞልቬር፣ እርሳቸዉ ነገሩኝ ብሎ
የጻፈው፣ አንድ ጓደኛው እቤቱ መጥቶ ወደ አንድ ሰዓት ገደማ እርሳቸው አንድ መጥፎ ነገር ይሆናል የሚል ስሜት
ተሰምቷቸው መሔዱን ቢቃወሙም ይዞት ሔደ፤ በዚያውም ቀረ የሚል ነው::
እንግዲህ ስለ እዛች ዕለት ከቤት አወጣጡ የቀረበው መረጃ የተጋጨ ስለሆነ ወይ ስልክ ደውሎ ጠራውና ሔደ ወይም
መጥቶ ይዞት ሔደ ይበሉ፣ አንዱን ይምረጡ የሚል ነበር የኔ የዚያን ወቅት ጥያቄ::
ሐቁ ግን፣ በዚያች ዕለት እንዳጋጣሚ ሆኖ፣ ስልክ አልደወልኩለትም፣ ቤቱም አልሔድኩም ነበር:: ምክንያቱም፣ የአዲስ አበባ
ክልልን የዐሥር ዓመት የአብዮት ታሪክ የሚያዘጋጅ ኮሚቴ ውስጥ ተሳታፊ በመደረጌ፣ የሥራ ውጥረት ገጥሞኝ አመሽ ስለ
ነበረ ነበር::
በዚያችው ምሽት ግን፣ ስድሰት ኪሎ በሚገኘው በአዲስ አበባ ኢሠፓአኮ በስብሰባ ቢሮ ሌሎቹ ከሔዱም በኋላ አመሻሽቼ
ወደ ቤቴ ስጓዝ ማምሻ ቦታችን አካባቢ ስደርስ፣ ‹ለመንገድ› ለማለት በተለመደችው ቦታችን ለማቆም አዙሬ አቆምኩ:: አንድ
ወጥ ጽሑፍ ለማቀናበር እንድንችል በቀረቡልን የየቀበሌ፣ ከፍተኛ፣ ቃጣና እና የተቋማት የ10 ዓመታት የታሪክ ዘገባ
መረጃዎች ጭንቅላቴ ተሞልቶና ስቆዝም ቆየሁ:: ወደ ሦስት ሰዓት አካባቢ ይመስለኛል ፣ የበዓሉን የመኪና ክላክስ ሰምቼ ዞር
ስል፣ መኪናው ውስጥ አየሁት:: የመጣበት አግጣጫ የቤቱ ስላልነበረ፣ የት እንዳመሸ ገመትኩ:: መኪናዋን ባለችበት ትቶ፣
በእግሩ መንገዱን ረጋ ብሎ አቋርጦ መጣና እኔ መኪና ውስጥ ገባ:: ብዙም የረባ ነገር የምናወራው ስላልነበረን ይሆናል ትዝ
የሚለኝ የለም:: እንደኔው ደከም ያለው መሰለኝ:: ካሰብኩት በላይ በመቆየቴና እሱም የሚሔደው ወደ ቤቱ ስለነበር ብዙ
አልቆየንም:: ሃያ ቢበዛ ሠላሳ ደቂቃ ቢሆን ነው:: መኪናዬን አዙሬ መኪናው ጎን አቁሜለት ሲወርድ እኔ ወደፊቴ ቀጠልኩ::
እየተጠባብቅን አልነበረም የምንሔደው ሁሌም ቢሆን::
ስለዚህ፣ ተቀጣጥረን ሳይሆን በእንደዚያ ዐይነት አጋጣሚ ግን ተገናኝተን ነበር ያችን ዕለት::
አሁን ደግሞ በአበራ ለማ በተበተነው የ16 ገጽ ሐተታ ውስጥ በገጽ 6 ላይ ጓድ ቁጥር ኀምሳ ሦስት ከተሰኘ ባለሥልጣን፣
‹‹…ወደ ማታ በዓሉን የደህንነት ሰዎች ይዘውት እንደሄዱ ከቤተሰቡ ሰማሁ…›› የሚል ባለቤቲቱን ያይን ምስክርነት የሚሰጡ
የሚያስመስላቸው ‹መረጃ› ያስነብበናል:: ምን ማለት ነው; በእርግጥ ባለቤቲቱ ለባለ ሥልጣኑ ይኸን መረጃ ሰጥተዋል ሊለን
ነው ዐላማው; ሞኙ በሬ ሆይ ሣሩን አየህና ገደሉን ሳታይ ሆነበትሳ !
ፍቱን፦ በዓሉ እርሶ ጋ ከመድረሱ በፊት የት ቆየ ብለው ነበር የገመቱት?
አቶ አስፋው፦ ጥቂት ቀደም ብሎ እዚያው አካባቢ ወዳጅ እንደነበረው ተገንዝቤ ነበር ::
ፍቱን፦ የማን ቤት ነው ?
አቶ አስፋው፦ እሱን አላውቅም ::
ፍቱን፦ ወንድ ሴት?
አቶ አስፋው፦ ሴት::
ፍቱን፤ በዚያች ዕለት ምሽት እዚያ ቆይቶ ከተመለሰ በኋላ ነበር ከእርሶ ጋር የተገናኛችሁት?
አቶ አስፋው፦ እንደዚያ ነበር አመጣጡን ሳይ የገመትኩት::
ፍቱን፦ የቅርብ ጓደኛ እንደመሆንዎ ምናልባት ለመምከርም ለመገሠጽም አልሞከሩም?
አቶ አስፋው፦ በአዘቦቱ ከምንወያይባቸው ርእሰ ጉዳዮች ውጭ ነበረ:: የእኔና የርሱ ቁልፍ ጉዳይ ድርሰትንና ተዛማጅ
ጉዳዮችን የሚመለከት እንጂ ሌላውን የሕይወቱን ክፍል የግሉ ብቻ አድርጌ ነበር የማየው:: ከዚያ ያለፈ ነገር እርሱ
በአጋጣሚ በሚያነሣቸው ጉዳዮች ነው የምናተኩረውና ይኸ ተነሥቶ አያውቅም፡፡
ፍቱን ፦ እርሶና በዓሉ በየሳምንቱ ሮብ ካልሆነ ኀሙስ አለዚያ ዐርብ ትገናኙ የነበረበት የተለየ ምክንያት ነበራችሁ?
አቶ አስፋው፦ አዎን፤ እኔንና እርሱን የሚመለከት ትንሽ የግል ጉዳይ ነበረች::
ፍቱን፦ አሁን መግለጽ አይፈልጉም?
አቶ አስፋው፦ ከዋናው ጉዳያችን ጋር ቀጥታ ግንኙነት የሌለውና ለማንም የሚጠቅም (ወይም የሚጎዳ) መረጃ አይደለም::
ግን የግል ነገር ነው::
ፍቱን ፦በዚያች ምሽት ስንት ሰዓት ላይ ተገናኛችሁ?
አቶ አስፋው፦ ወደ ሦስት ሠዓት ግድም ነው :: በትክክል አላሳተውስም ::
ፍቱን፦ የዚያን ምሽት የበዓሉ አለባበስ እንዴት ነበር?
አስፋው፡- እንደ ሁሌውም ሽቅርቅር ያለ ነበር ማለት ይቻላል:: ቡላ ቀለም የሆነ ሙሉ ልብስ መሰለኝ:: ልብ ብዬ
ያተኩርኩበት አልነበረም:: ዐይኑ ላይ ኦይንትመንት ብጤ ያየሁ መስሎኛል::
ፍቱን፦ ድካም ያዩበት ለምን ይመስልዎታል?
አቶ አስፋው፦ እንደርሱ ንቁ የሆነ ተንቀሳቃሽና በሥራ ውጥረት ውስጥ የቆየ ሰው ያለ ፈታኝ ሥራ ውሎ ሲያመሽ ይህ
ዐይነት ስሜት የሚያድርበት ይመስለኛል:: ጊዜውም እየተማሸ በመሔድ ላይ መሆኑን ማሰብ ይኖርብናል:: የኔም መንፈስ
ብዙ የነቃ መሆኑን እርግጠኛ አይደለሁም:: በውሎዬ ስላጋጠሙኝ አንዳንድ መንፈስ መሳጭ ስሜት ቀስቀሽ ስለሆኑ የቀበሌና
የከፍተኛ የታሪክ ሰነዶችና መረጃዎች እርሱ ከነበረበት ሁኔታ ለመወያያ አመቺ አልነበሩና የሚነሡ አልነበሩም ከርሱ ጋር::
ፍቱን፦ ከበዓሉ ሁኔታ ወይም ከአካባቢው የታዘቡት የተለየ ነገር ነበር?
አቶ አስፋው፦ ምንም የታዘብኩት ነገር አልነበረም:: መኪናዬን ሲያይ ምንም ሳይል ዐልፎኝ መሔድ ስለማይችል መጣ
እንጂ ጊዜው ለተለምዶው ዐይነት
ውይይት አመቺ ሆኖ አልነበረም የመጣው:: እንዳልኩህ ያኔ ሰዓቱ ሁለታችንም ወደየቤታችን ለመሔድ መንፈሳችን
ያዘነበለበት ሁኔታ ነበር::
ፍቱን፦ ስንት ሰዓት አካባቢ ተንቀሳቀሳችሁ?
አቶ አስፋው፦ ከሦስት ሠዓት ቢያልፍም ብዙ አይመስለኝም::
ፍቱን፡- ስትለያዩ፣ በዓሉ ወዴት እንደሚሔድ ያውቁ ነበር?
አቶ አስፋው፦ ወደ ቤቱ ነዋ! የእኔን መኪና አይቶ የቆመው ወደ ቤቱ አግጣጫ እየነዳ ሳለ ነበር:: መኪናው ዘንድ ሳደርሰው
ጉዞውን ነው የሚቀጥለው:: ለእኛ ያቺ ምሽት እንደሌሎቹ ሁሉ አንድ ሌላ ምሽት ነበረች! ከመምጣቱ ዐምስት
ደቂቃዎች ቀደም ብዬ ሔጄ ቢሆን ኖሮ፣ በዚያች ማታ አንተያይም ነበር::
ፍቱን፦ የበዓሉን መሰወር የሰሙት በምን ሁኔታ ላይ ሆነው ነበር?
አቶ አስፋው፦ በማግሥቱ ጧት ወደ ሁለት ሰዓት ተኩል አካባቢ ነበር:: ወደ አዲስ አበባ ኢሠፓአኮ ለመሔድ እየተደራጀሁ
ሳለ፣ ባለቤቱ ደወለችልኝ ::
ፍቱን፦ወ/ሮ አልማዝ፣‹‹በዓሉ የማታ ማታ ወደቤት ይመለሳል ብዬ እስከ እኩለ ሌሊት ድረስ ብጠብቅም የውሃ ሽታ
እንደሆነ ቀረ፡፡ ቢቸግረኝ አስፋው ቤት ደወልኩ፡፡ ሚስቱ ስልኩን አነሳች፡፡ ’…አስፋው እቤት ገብቷል?…’ ስል ጠየቅኋት፡፡
’…አዎን ገብቷል…’ አለችኝ፡፡ ይሄኔ ግራ በመጋባት፤ ’…ባሌን ከቤት ጠርቶ ወስዶት የት ጥሎት ነው እሱ ተቤቱ የገባው?…’
እያልኩ አፋጠጥኳት፡፡ ቀጥዬም ’እስኪ አቅርቢልኝና ላናግረው…’ ስላት፤ ’የገባ ምስሎኝ ነበር እንጂ አልገባም’ ብላ
የመጀመሪያ ቃልዋን አጠፈችብኝ፡፡ የስልክ ንግግራችንም በዚሁ ተቋጨ›› ብለዋል እውነት ነው?
አቶ አስፋው፦ ሐሰት ነው
ፍቱን፦ መሥረያ ቤት ነበር የደወሉት?
አቶ አስፋው፦ አዎን፣ ኢትዮጵያ መጻሕፍት ድርጅት እኮ ነው ! እዚያኛውማ ገና ልሔድ ነው ::
ከዚያ፣ ‹‹በዓሉ እኮ ትላንት ማታ አልገባም:: አልተገናችሁም ነበር ወይ;›› ስትለኝ ያመሸበት ትዝ ብሎኝ ነበርና፣ ‹‹አይቸዋለሁ፣
ግን›› ብዬ የምለው ጠፋኝና፣ ‹‹አሁን የምሔደው አንድ ትልቅ ባለሥልጣን ዘንድ ለስብሰባ እንዲህ ዐይነቱን ነገር ለማጣራት
ችሎታ አለው:: በከተማው ውስጥ የሚካሔደው ነገር ሁሉ የሚዘገብለት እርሱ ስለሆነ አነጋግሬ ሁኔታውን አጣራለሁ››
አልኳት:: አዲስ አበባ ኢሠፓአኮ ጽሕፈት ቤት እንደረስኩ በቀጥታ ወደ በላይ ኀላፊው ቢሮ ገብቼ ነገሩን አነሣሁ:: ‹‹አንድ
ቦታ (ጾታን ጠቁሞ) አድሮ ይሆናል ነገ ብቅ ይላል ››አለኝ አቃሎ:: እኔም ይኸ ሊሆን እንደማይችልና ማታ ከዚህ ወደ ቤቴ
ስሔድ እንደተገናኘንና ስንለያይ ወደ ቤቱ እያመራ እንደ ነበር አጠንክሬ ገለጽሁ:: ከዚያ፣ ቆይ ብሎ አንድ ቦታ ደውሎ ጥቂት
ከተነጋገረ በኋላ ምንም መረጃ እንደሌላቸው ገለጸልውልኛል፣ አሁንም ጥቂት አሰብ አደረገና ሌላ ቦታ ደውሎ ተናጋገረ::
ውጤቱ ምንም ለውጥ አልነበረውም:: በዓሉን የሚያህል ሰው ጠፍቶ የአዲስ አበባን አጠቃላይ ሁኔታ የማወቅ ዐቅም ካለው
ከዚህ ቢሮ ተሰውሮ ብዙ እንደማይቆይ ተስፋ ያለኝ መሆኑን ተናግሬ ወደ ስብሰባ ቢሮው ሔድኩ ::
ፍቱን፦ ያ ባለሥልጣን ማን ነበር ?
አቶ አስፋው፦ ኮማንደር ለማ ጉተማ ነበር :: በትምህርት ቤት ዕውቂያ ስለነበረን ነው የሚቻለውን ያህል ሊጥርልኝ ይችላል
የሚል ተስፋ የነበረኝ ::
ፍቱን፦ ኮማንደር ለማ የት እና የት የደወሉ መሰለዎት?
አቶ አስፋው፦ ስለ አዲስ አበባ የየዕለት ሁኔታ የሚያሳውቁት አካላት ዘንድ ነው ብዬ ነበር የገምኩት::
ፍቱን፦ ደህንነት መሥሪያት ቤት ማለት ነው?
አቶ አስፋው፦ ሊሆን ይችላል:: ልዩ ክፍሎችም ሊኖሩት ይችላሉ፣ አላውቅም::
ፍቱን፦ ያንለት ወ/ሮ አልማዝን በድጋሚ አግኝተዋቸው ነበር?
አቶ አስፋው፦ አዎን፣ በስልክ ይሁን በግምባር፣ ምንም ፍንጭ ለጊዜው ባላገኝም፣ ተስፋ እንዳልቆረጥኩ ነግሬያት ነበር ::
ፍቱን፦ የበዓሉን መሰወር ጉዳይ እርስዎ የምር ነበር ያዩት ወይስ …?
አቶ አስፋው፦ አዎን ግን ደግሞ አንዳንድ የገለጻቸውን ሁኔታዎች የሚከርር አይሆን ይሆን የሚል ልብ ከፋይ ስሜት
መነሻው ላይ ልቤን ያሟግት ነበር:: ለምሳሌ፣ ቀደም ብሎ ባንድ ወቅት ታሰረ የሚል ወሬ ተነዝቶ ነበር:: ያን ወቅት ኢትዮጵያ

መጻሕፍት ድርጅት ድረስ ይመጣ በነበረበት ጊዜ፣ ልክ ከእኛ ዘንድ ተመልሶ እንደሔደ፣ አንድ ሰው ደውሎ ስለ መታሰሩ
ነገረኝ:: ግን፣ እኛ ዘንድ መጥቶ እንደነበርና ዝም ብሎ ወሬ ነው ማለቴን አስታውሳለሁ:: ከዚያ በኋላም እርሱው ከቤተ
መንግሥት አካባቢ ቤቱ ተደውሎ ስለ ደህንነቱ የተጠየቀ መሆኑን ነግሮኝ ነበር:: ሆኖም ሙሉ ለሙሉ መተማማን አስቸጋረ
ነበር:: ከኦሮማይ ጋር መያያዙ ታሳቢ ጉዳይ ስለሆነ ስለ ነገሩ ክብደት ማመን ፍጽም አልነበረም::
ፍቱን፦ መንግሥቱ ናቸው የደወሉት?
አቶ አስፋው፦ ማን እንደሆነ ተነግሮት እንደሁ አልነገረኝም:: እኔ ግን ሊሆን ይችላል ብዬ አላሰብኩም፣ አልመሰለኝም::
ፍቱን፦ ስለዚህ የምር ይሆናል ብለው አላሰቡትም ነበር?
አቶ አስፋው፦ አጽናኝነት ያላቸው ምልክቶች ሆነው ቢታዩም ቀላል አድርጎ የሚታይ ነገር አልነበረም :: እርግጥ መንፈስን
አዋዥቋል:: ከዚያ ለመንግሥት መሥሪያ ቤቶች ፈልጉ አፋልጉ የሚል ቴሌግራም እንደተበተነ ሰማሁ:: በዚያው ሰሞን
ከበዓሉ ጋር ቅርብ ግንኙነት አላቸው ተብለው ከታሰቡ ውስጥ ይመስለኛል ሦስት ሰዎች በተናጠል ተጠርተው ስለ ጉዳዩ
የሚጠረጥሩት ነገር እንዳለ እንዲጠቁሙ ፍንጭ ካገኙ ደውለው እንዲያሳውቁ ስልክ ቁጥር ተሰጣቸው :: ከሦስቱ ሁለቱ
ባለቤቱና እኔ ነበርን ::
ፍቱን፦ ማን ነበር የጠየቀዎ?
አቶ አስፋው፦ መልኩን እንጂ ስሙን አላውቀውም ::
ፍቱን፦ ወ/ሮ አልማዝ በርስዎ ላይ ቅያሜ ለምን ሊያድርባቸው ቻለ?
አቶ አስፋው፦ በዓሉ ከተሰወረ በርከት ያለ ቀናት ቆይቶ፣ ወ/ሮ አልማዝ ‹‹የበዓሉ መኪና ቃለቲ መንገድ ላይ ቆማለች አሉ፣
ሔደን እናምጣት›› አለችኝ ቤቴ ለመጀመሪያ ጊዜ ደውላ :: ‹‹ይኸንማ ማድረግ አንችልም:: በተሰጠሸ ስልክ ቁጥር ደውለሽ
አሳውቂ እንጂ ከነረው ሁኔታ እንደፈለገን ማድረግ አንችልም ::››፣
ከዚያ በነገሯ ሁሉ የማላውቃት ሰው ዐይነት ሆነችብኝ:: ከመነሻው ብዙ ትውውቅም አግባብም አልነበረንም:: የኔ ጉዳይ
ከባዓሉና ከድርሰቱ ጋር እና በውጭ ነበር ::
ከሥራ ከታገደ በኋላ ቤቱ መሔድ ግድ ሆነ ፤ እኔና እርሱ መገናኘት የምንችልበት ዋና ቦታ ያ ብቻ ሆና ነው :: እርሱ ሳይኖር
ቤቱ ከማን ለመወያየት ነው እንድሔድ ይጠበቅ የነበረው:: ቀድሞም ቤት ለቤት የመጠያየቅ እና ያን ዐይነት ማኅበራዊ
ግንኙነት አልነበረንም :: ያኛው ለሁለታችንም ሌላ ዐውድ ነበር :: እርሱ የራሱ እኔም የራሴ ነው የነበረን::
ስለዚህ፤ ለዚህ እና ለተለያዩ የእርሷ ውንጀላዎችም ሆኑ ስሞታዎች
ትክክለኛው መልሱ የሚገኘው ከእኔና ከበዓሉ የግንኙነት ዐይነትና መሠረታዊ ባሕርይ ነው :: ነገር በመደጋገም አዲስ እውነት
አይፈልቅም:: ስለ እርሳቸው አመለካከት ትክክሉን ነገር ለማግኘት የምር ለማወቅ በየጊዜው የሰጧቸውን በርካታ ቃለ
መጠይቆች እያገናዘቡ ማንበብ ነው::
አሁን የተበተነውና መጽሔቶችን እያጣበበ ያለው ሰፊ ሐተታ ገሐድ ያወጣው ቁምነገር፣ ሚያዝያ 8 ቀን 1989 በወ/ሮ
አልማዝ ስም ከመነሻ የውንጀላ ጽሑፍ አንሥቶ ሐተታው ውስጥ በስማቸው የወጣው ሐሳብ ሁሉ ከነቃላቱ የእርሳቸው
እንዳልነበረ ነው :: ሰው ትኩረት እንዲሰጠው የበዓሉን ስም ሽፋን አድርጎ የራሱን ቂም፣ በቀልና እና ብሶት ለማሰተላለፊያ
የተጠቀመበት ሆኖ ነው የሚገኘው ጽሑፉን በታኙ :: እውነት ፈላጊ ፈልፍሎ እንደሚደርስበት ጥርጥር የለኝምና፣ ይኸኛውን
በዚህ ጨርሻለሁ::
ፍቱን፦ በዚህ ጉደይ ፍርድ ቤት ቀርበው ተጠይቀው ያውቃሉ?
አቶ አስፋው፦ አልተጠየቅሁም:: የፍርድ ቤትን ፍጹም አሉቧልታ መች ይቋቋመዋል; ቀደም ሲል አሉቧልታን ይዞ ወደ
መገናኛ ብዙኃን መሔድ ይቀል ነበር:: አሁን ያ በር እየጠበበ ይመስለኛል::
ፍቱን፦ በእርስዎና በበዓሉ መካከል ቅያሜ ወይንም አነሥተኛ ቁርሾ ነበር?
አቶ አስፋው፦ የምን ቁርሾ አመጣህብኝ:: ቀድሞ መች ለበቂ ጊዜስ ተገናኝትን:: በጽሑፉ አድናቂው ነኝ ፤ ሒሳዊ ትችት
የሚጠላ ሰው አልነበረም:: በሙያና በመሥሪያ ቤት የተለያየን ነን:: ስለዚህ፣ ላልከው ነገር ሰበብም አልነበረም::
ፍቱን፦ ኩራዝ እንዲገቡ በዓሉ ከፍተኛ ውትወታ አድርጎ ፍቃደኛ ሳይሆኑ ቀርተው፣ ኋላ በምን የተለየ ምክንያት እዚያ
ገቡ?
አቶ አስፋው፦ ወደ ኩራዝ የመግባቱ ጥያቄ ረዘም ያለ የጊዜ ሒደት የነበረውና ከዚህ ቀደም መልስ የሰጠሁበት ነው:: በዚህ
ረገድ በዓሉ ከብዙዎች አንዱ ነበር::
ይሁንና፣ የኩራዝ አሳታሚ ድርጅት ዋና ሥራ አስኪያጅ የነበረው ተስፋዬ አያሌው አንድ የጥበባት ጉዳይ መጽሔት
ለመመሥረት ተነሣሥቶ ከያለበት ጽሑፍ የሚያቀርቡ ሰዎች ሲያፈላልግ በዚያ ሳቢያ ተገናኝተን ተዋወቅን:: ከዚያ፣ ሥነ
ጽሑፍን ለማሳደግ ከልብህ ካሰብክ፣ አሰታሚ ዋና ክፍሉን አጠናክረህ ምራው ብሎ፣ ሊያሠራ የሚችል ሁኔታ
እንደሚያመቻችልኝ አሳመነኝ:: እኔም በኢትዮጵያ መጻሕፍት ድርጅት ላራት ዓመታት ያህል በተግባርም በንባብም
የቀሰምኩትን ዕውቀትና ልምድ ሰፋ ባለ መድረክ ተግባር ላይ ለማዋል አጓጓኝ:: ከባድ ውሳኔ እያደረግሁ መሆኔም እየተሰማኝ
ነበር :: ይሁን እንጂ ስበቱ አየለና፣ ተደራድሬ የአሳታሚ ዋና ክፍሉ ኃላፊ ሆኜ ተቀጥሬ ገባሁ::
ከ1977 እስከ 1983 የነበረውን የኩራዝ አሰታሚ ድርጅት እንቅስቃሴና ተጨባጭ ውጤት ሳሰተውል ያደረግሁት ትክክለኛ
ውሳኔ እንደነበረ እና በውጤቱም እርካታ ይሰማኛል::
ፍቱን፦ ወዳጅዎን የኢትዮጵያ መጻሕፍት ድርጅት ባለቤት እንዴት አሳመኗቸው?
አቶ አስፋው፦ ከእርሱ ጋር ቀደም ሲል ከገንዘብ ሚኒስቴር ዘመኔ ጀምሮ ነበርና የምንተዋወቀው፣ ስለሁኔታዎች የጋራ
መግባባት ነበረን:: በዚያው ተወስኜ እስከ ዘለቄታው እንደማልቆይ አስቀድሞ የታወቀ ነበር:: ስለዚህ ለመልቀቅ ችግር
አልነበረም ::
ፍቱን፦ ለበዓሉ መሰወር ከኦሮማይ ሌላ መንሥኤ ይኖራል?
አቶ አስፋው፦ የግንኙነታችን አግጣጫ ሥነ ጽሑፍ አንድ ጠበብ ያለ ገጽታው ነው:: ከዚያ ውጭ ያለ ገጽታው ነው
የሚበልጠው፣ የሚሰፋው:: በዓሉ የመንግሥት ባለሥልጣን የነበረ በዚያ አግጫም ኃላፈነቶች ነበሩበት :: ስለዚህ ከቁንጽል
እይታ ተነሥቶ ትልቅ ድምዳሜ መድረስ አስቸጋሪ ነው::
ፍቱን፦ በእርሶ ላይ ከሚሰጡ አስተያየቶች መካከል አንዱ፣ አቶ አስፋው ሰኔና ሰኞ የሚባለው ገጥሞባቸው ነው እንጂ ፣
ጓደኛቸውን አሳልፈው የሚሰጥ ሰብእና የላቸውም የሚል ሲሆን፣ ሁለተኛው ደግሞ፣ አቶ አስፋው ጓደኛቸውን የሚሸጡ
ሰው አይደሉም፣ ነገር ግን፣ የዚያች ዕለት ምሽት ያዩትን አይተው ለሕይወታቸው ሠግተው ዝም ብለዋል የሚል ነው?
አቶ አስፋው፦ በኔ ትሑት አስተያየት ከግለሰቡ ሰብእና ተነሥቶ፣ አንድ ሰው ምን ዐይነት ተግባር ለመፈጸም እንሚችል እና
እንደማይችል ለመመዘን ለማየት መነሣት ትክክለኛ የብየና መንገድ ነው ብዬ አስባለሁ:: እኔን በሚመለከት ከነገርከኝ
የሁለተኛው ወገን መላምት እንዳጋጣሚ ሁኖ የተከሰተ ሐቅ አልነበረም:: ያመሸንበት አካባቢ ለዚህ ግብ የሚመረጥ ይሆናል
ብዬ አልገምተውም:: የሆነው ሁኖ፣ ያችን ምሽት በዓሉን የሚመለከት እኔ ያየሁትና ያስፈራኝ ክስተት አልነበረም:: ስለዚህ፣
አይቼ ዝም ያልኩት ወይም የደበቅሁት ነገር እንደሌለ በእርግጠኝነት እናገራለሁ:: ይኸን መቀበል አለመቀበል የእምነት ጉዳይ
ሊሆን ይችላል::
ነገር ግን፣ ከዚህ ዘልዬ አጋጥሞኝ የነበረ ቢሆን ኖሮ የሚለውን ማሰብ አያስልገኝም:: አላጋጠመም በቃ! ብዬ አቆማለሁ::
ፍቱን፦ ሰው በበዓሉ መሰወር እኔን ተጠያቂ አድርጓል የሚል ቅሬታ ወይ ምሬት አድሮቦታል;
አስፋው፦ ፈጽሞ! ኅሊናዬ ንጹህ እና የውስጥ ሰላም ያለኝ ሰው ነው :: ከዚያ ቀጥሎ ደግሞ፣ በሕግ ፊት ከምኑም ነጻ የሆንኩ
ዜጋ ነኝ:: ከታወቁት ሁለት ወንጃዮቼ ሌላ የማውቀው ሌላ የለም:: የሚጠረጥር ቢኖር መብቱ ነው:: እውነቱን ፈላጊ ከሆነ
ይደርስበታል ብዬ አስባለሁ::
ፍቱን፦በዓሉን በተመለከተ ሕሊናዎ ነጻ ነው?
አቶ አስፋው፦ Absolutely, ምንም:: በበዓሉ ግርማ ጉዳይ ላይ ከሕሊና ዕዳ ነፃ ነኝ:: ለምኑ ብዬ እኮ ነው የምልህ? እንዲህ
አይነት ሁኔታ ውስጥ የሚጨምረኝን ነገር ለምን አደርጋለሁ? እኔ ሰዎች በጥረታቸው ሲሳካላቸው ደስ ይለኛል:: የሆነ
እርካታ ይሰማኛል፣ ይሄ ባህሪዬ ተቃራኒ ስሜትና ዝንባሌ ያላቸውን ሰዎችን ያናድዳቸው ይሆን ብዬ ራሴን እጠይቃለሁ::
እነሱ ተመኝተውት ያጡትን እኔ ሳልፈልግ አግኝቼ ይሆን?
ፍቱን፦ አቶ አበራ ለማ ጋር ከዚህ በፊት ቅራኔ ነበራችሁ?
አቶ አስፋው፦ እኔ ከእሱ ጋር ቅራኔ ውስጥ ገብቻለሁ ብዬ አስቤ አላውቅም:: የተገናኘነው ኢትዮጵያ መጽሐፍ ድርጅት ሆኜ
“ሕይወትና ሞት” የምትለው መጽሐፍ እንዲታተምለት የበኩሌን አስተዋጽኦ አድርጌያለሁ:: የ“ማለዳ ስንቅ” የምትለዋን
ኩራዝ እንድትታተም አስተዋጽኦ አድርጌያለሁ:: በድርሰት በኩል ግንኙነታችን ይሄ ነው::
አንድ ጊዜ ኩራዝ የጀመርናት መጽሔት የመጀመሪያው ሕትም የመሆኑ ጽሑፎች ሰዎች እዲያመጡልን በአዘጋጁተ በስብሐት
ገ/እግዚአብሔር ጥሪ ተደርጐ ስለነበር ጽሑፋቸውን ካመጡልን ሰዎች መካከል አበራ ለማ አንዱ ነበር::
የሆነ ቀን ስብሐት ቢሮዬ ይመጣና “ይሄንን ነገር አንብበው፣second opinion እፈልጋለሁ” ብሎ የአበራ ለማን ጽሑፍ
ይሰጠኛል:: አነበዋለሁ:: የተጻፈው “ሂስ” ተብሎ ነው:: ሂሱም የሚካሄደው በታዋቂው ገጣሚ በሰይፉ መታፈሪያ “የተስፋ
እግር ብረት” ውስጥ ባለ አንድ ግጥም ላይ ነው:: እንደአጋጣሚ “የተስፋ እግር ብረትን” ሰይፉ መታፈሪያ ሸልሞኝ እጄ ላይ
ስለነበር አውቀዋለሁ:: ሂሱን ሳነበው ትንታው ጥሩ አልነበረም:: ያን ጊዜ አበራ ለማ ገና የኢትዮጵያ ቋንቋዎችና ሥነ ጽሑፍ
መግባቱ ነበር መሰለኝ:: የተማረውን ተግባራዊ ለማድረግ ነው መሰለኝ ያንን ጽፏል:: መደምደሚያውግን ፍጹም ትክክል
ስላልነበረ ይሄንኑ ለስብሐት ነበርኩት:: ስብሐትም የእኔም ሃሣብ ነው ብሎ ተስማማ:: በሁለቱም መጽሐፎቹ ሳቢያ
እንተዋወቃለን በሚል ደውለን አናናግረው ብለን ደውዬ ነበርኩት:: በፍፁም አልተስማማም:: “ተሳስተሃል” አለኝ::
ፍቱን፦ አቶ አበራ ለማ በግጥሙ ላይ የሰጡት ድምዳሜ ምን ነበር?
አቶ አስፋው፦ የግጥሙ መልዕክት ብር ቁፈራ ነው የሚል ነበር የእሱ ድምዳሜ:: በእርግጥ ግጥም ገጣሚ ስለብር መቆፈር
ሊጽፍ ይችላል:: አበራን ወደዚያ ድምዳሜ የመራው ግን የሰይፉ አንዳንድ ፊደሎችን የመደጋገም ስልቱ ነው:: በዚያ ላይ
ተመስርቶ የፈጸመው ስህተት ነው እኔ የመሰለኝ::
(ግጥሙን ቀጥሎ ያለው ነው)
አድካሚ የሕይወትን መልክ ፍለጋ
እፍ እፍ፤ እፍ የጉሽ ገፈት
የጥራት ከለላ
እንትፍትፋት::
..
እፍ እፍ ስልባቦት
የወተት ላይ ውፍረት
እኝካት::
..
እፍ እፍ ግግርት
የውሃ ላይ ቅርፊት
አረንጉዋዴ በቀልት::
..
እንደ ጉሽ ገፈቱ
እንደ ስልባቦቱ
የውሃ ግግርቱ
..
እንደዚያ ደዚያ
እፍልኝ ምሥጢር ከለላ
ሰዋዊ ዐይነ – ጥላ::
..
የሕይወት ምሥጢር
በዘመናት ክምር
ቅበርብርብርብርብር
(እሱን ነው እምቆፍር)::
ሰይፉ መታፈሪያ ፍሬው (መስከረም 1969 ዓ.ም)
ፍቱን፦ ከዚህ ሁሉ በኋላ ልትግባቡ አልቻላችሁም?
አቶ አስፋው፦ ‹‹ተሳስተሃል››አለኝ:: ነገሩ እኔ እኮ የስነ ጽሑፍ ተማሪ ነኝ ነው:: “አይ በአንተ ድምዳሜ ያልተስማማሁት እኔ
ብቻ ሳልሆን የመጽሔቱ አዘጋጅ ስብሐትም ጭምር ነው፣ ስብሐትም እንደዚሁ ነው ያሰበው›› አልኩት:: “ሁለታችሁም
ተሳስታችኋል” ሲለኝ፣ “እኛ ስህተት ነው ብለን የምናስበውን መተው እንችላለን፣ ወይም ደግሞ ከComment ጋር
ልናቀርበው እንችላለን:: ‹‹እንዲህ ብለነው ነበር፣ አንባቢ ራስህ ፍረድ›› ብለን ማውጣት እንችላለን፣”ብዬው በመሐሉ፣‹‹
ገጣሚው ራሱ ስላለ ልደውልለት›› ስለው፣ ‹‹ደውልና ጠይቀው›› አለኝ::
ሰይፉ መታፈሪያን ደውዬ የአበራን ድምዳሜ አነበብኩለትና አስተያየቱን ጠየቅኩት::
“እንዴ ብሩን ከየት አመጣችሁት?” ነው ያለው:: ግጥሙ ውስጥ እኮ ብር የለም፣ ማለቱ ነው::
ይሄንን ነገርኩት::
አበራ ለማ አሁንም፣“እሱም ተሳስቷል” አለኝ:: ‹‹ባለግጥሙ?›› ስለው፣ ‹‹አዎን አያሲው እኮ ደራሲው ያላየውን የግጥሙን
አንድ መልክ ፈልፍሎ ያወጣል›› አለ:: ይሄንን መርህ እንደ መርህ አውቀዋለሁ:: እውነትም ይሆናል፣ ይሄኛው ግጥም ግን
በጣም ግልጽ ነው:: የመጀመሪያው አንጓ፣ የሁለተኛው፣ የሶስተኛው አንጓ በግልጽ ያስቀምጠዋል:: አራተኛው ላይ ሲመጣ
ያንኑ ነው:: ያ የሚቆፈረው የህይ ወትን ሚስጢርን ለማግኘት ነው፣ የሚል ነው:: ግጥሙ ራሱ ግልጽ ነው ››አልኩት:: ይሄ
ነው ያስቀየመው::
የነገሩ መቋጫ ይሄ ብቻ አይደለም:: ለካ ማታ ዩኒቨርሲቲ ሲሄድ ለጓደኞቹ “ሁለት ግጥም የማይገባቸው ሽማግ ሌዎች” እያለ
ወረፍ አድርጐናል:: ሌላው ክፋቱ በዚያን ሰዓት ፣ ስለ ሁለቱ “ግጥም የማይገባቸው ሽማግሌዎች” ማንነትና ስለየትኛው
ግጥም ማለቱ እንደሆነ እየጮኸ ሲያወራ በዚያ በኩል ያልፍ የነበረ አስተማሪው ይሰማዋል ፣አስተማሪው ደግሞ ግጥሙን
ያውቀዋል:: ወዲያውወደ አበራ ቀረብ ብሎ ፣ “የሚያሳፍሪው ነገር ምን እንደሆነ ታውቃለህ ? አንተ የእኛ ተማሪ ነህ መባሉ
ነው” ብሎት ይሄዳል:: ይኼ መቼም ቅስም የሚሰብር ነው:: ያቺ ትሆን እንዲህ የምታደርገው ብዬ አስባለሁ:: ያ ነው እንግዲህ
በእኔና በእሱ መካከል ተከሰተ የምለው ነገር::

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይልና ኤሌክትሪክ አገልግሎት ሀብታቸውን በግልጽ እንዲለዩ የዓለም ባንክ አሳሰበ

0
0

Ethiopian Electric Power Corporationየቀድሞው የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ኮርፖሬሽን ለሁለት ተከፍሎ የተፈጠሩት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይልና ኤሌክትሪክ አገልግሎት፣ ሀብታቸውን በግልጽ ለይተውና ተካፍለው የየራሳቸውን የሒሳብ መዝገብ እንዲይዙ የዓለም ባንክ ማሳሰቡን ምንጮች ገለጹ፡፡

የዓለም ባንክ ማሳሰቢያውን የሰጠበት ምክንያት ለአገር አቀፍ የኤሌክትሪክ ኃይል ቋት (Grid) ማጠናከሪያና ማስፋፊያ የሰጠው ብድር በአግባቡ ሥራ ላይ እየዋለ መሆኑን ለማረጋገጥ መሆኑ ተጠቁሟል፡፡

እ.ኤ.አ. በግንቦት 2012 የዓለም ባንክ ለኢትዮጵያ ብሔራዊ የኤሌክትሪክ ኃይል ቋት ማጠናከሪያ ፕሮጀክት የ200 ሚሊዮን ዶላር ብድር ከገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ሚኒስቴር ጋር ተፈራርሟል፡፡

በስምምነቱ መሠረት የቀድሞው የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ኮርፖሬሽን የፕሮጀክቱ ፈጻሚ ሲሆን፣ ፕሮጀክቱ ተግባራዊ መሆን የጀመረው እ.ኤ.አ. ጃንዋሪ 2013 መሆኑን መረጃዎች ያመለክታሉ፡፡

ሥራው ከተጀመረ በኋላ የኢትዮጵያ መንግሥት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ኮርፖሬሽንን ለሁለት በመክፈል ራሳቸውን የቻሉ ሁለት ተቋማትን ፈጥሯል፡፡ የተፈጠሩት ሁለት ተቋማት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይልና የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ናቸው፡፡

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በኢንጂነር አዜብ አስናቀ የሚመራ ሲሆን፣ ኃላፊነቱም የኃይል ማመንጫ ግንባታዎችን እንዲሁም የመስመር ዝርጋታዎችን የተመለከተ ነው፡፡ ሁለተኛው የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የኃይል ሥርጭትንና ጥገናን የተመለከተ ኃላፊነት ተሰጥቶት ማኔጅመንቱም በሁለት ዓመት ኮንትራት ለህንድ ኩባንያ ባለፈው ዓመት መሰጠቱ ይታወሳል፡፡

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ኮርፖሬሽን ለሁለት መከፈሉ የኃላፊነት መዛባትን ያስከትላል የሚል ሥጋት የገባው የዓለም ባንክ፣ ከገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ሚኒስቴር ጋር ወዲያውኑ ውይይት ማድረጉን ምንጮች ይገልጻሉ፡፡

የተደረገው አዲስ አወቃቀር የፕሮጀክት ትግበራውን ያስተጓጉላል፣ ተጨማሪ ወጪ ያስከትላል፣ በፕሮጀክቱ ከሚሳተፉ ኮንትራክተሮች ጋር ግጭት ይፈጥራል በሚል በቀረበ ሐሳብ መሠረት ቀድሞ በተፈረመው የብድር ስምምነት ውስጥ የሚካተት የመግባቢያ ስምምነት በመፈራረም ፕሮጀክቱ መቀጠሉን ምንጮች ይገልጻሉ፡፡

የመግባቢያ ስምምነቱ እስኪፈረም ድረስ መጠነኛ የሥራ መጓተት መፈጠሩን ለመረዳት ቢቻልም፣ አሁንም ቢሆን በሚፈለገው ፍጥነት ፕሮጀክቱ እየሄደ አለመሆኑን ምንጮች ያስረዳሉ፡፡

ለአብነት ያህልም የዓለም ባንክ ለፕሮጀክቱ ከፈቀደው 200 ሚሊዮን ዶላር ብድር ውስጥ፣ ፕሮጀክቱ በተጀመረ በአንድ ዓመት ከስድስት ወራት ውስጥ የተጠቀመው ዘጠኝ በመቶውን ብቻ እንደሆነ ይጠቅሳሉ፡፡

ሁኔታው ያሳሰበው የዓለም ባንክ ከሁለት ሳምንት በፊት ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሥራ ኃላፊዎች ጋር ፕሮጀክቱን በመገምገም ማሳሰቢያዎችን መስጠቱን ምንጮች ይገልጻሉ፡፡

የኢትዮጵያ አሌክትሪክ ኃይልና የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ግልጽ የሆነ የሀብት ክፍፍል አድርገው ባለመለያየታቸው፣ በአጭር ጊዜ ውስጥ የፋይናንስ አማካሪ ድርጅት በመቅጠር ሀብታቸውን እንዲለያዩና ግልጽ የሆነ የየራሳቸው የሒሳብ መዝገብ እንዲፈጥሩ ማሳሰቡን ምንጮች ገልጸዋል፡፡

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ፕሮጀክቱን ተግባራዊ በሚያደርግበት ወቅት፣ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ትብብርን የሚሹ ጉዳዮች የሚኖሩ በመሆናቸው እነዚህ ትብብር የሚሹ አካባቢዎች በግልጽ እንዲለዩ ባንኩ ማሳሰቡ ታውቋል፡፡

ጉዳዩን በተመለከተ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር አዜብ አስናቀን ለማግኘት የተደረገው ጥረት መሳካት አልቻለም፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የዋየር ቢዝነስ ሥራ አስፈጻሚ የሆኑት አቶ ቢትወደድ ገብረ አሊፍ ሥራው በአግባቡ እየተሠራ መሆኑንና በጥሩ ደረጃ ላይም እንደሚገኝ ይገልጻሉ፡፡

‹‹ሥራውን ተከፋፍለናል፡፡ ሥራውን ስንከፋፈል ሁሉም ወደሚመለከተው ይሄዳል፡፡ ነገር ግን አብሮ የመሥራትና የመተባበር ጉዳይ የሚቀር አይደለም፡፡ ምክንያቱም ሥራ ተከፋፈልን እንጂ ፍቺ አይደለም የፈጸምነው፡፡ እንዲህ ብንረዳው ይሻላል፤›› ብለዋል፡፡

የዓለም ባንክ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ኮርፖሬሽን ከመፍረሱ በፊት ከሰጣቸው ብድሮች መካከል ለየኢትዮ-ኬንያ የኃይል ማስተላለፊያ ፕሮጀክት የሚውል ግማሽ ቢሊዮን ዶላር ይገኝበታል፡፡ ነገር ግን ይህ ፕሮጀክት በአሁኑ ጊዜ በመግባባት እየተከናወነ መሆኑን ለመረዳት ተችሏል፡፡

 

Source:: Ethiopian Reporter

ከጥቅሙ ጉዳቱ ይበልጣል (ፕ/ር መስፍን ወልደ ማርያም)

0
0

መስፍን ወልደ ማርያም

ሐምሌ 2006

ፕ/ር መስፍን ወልደ ማርያም

ፕ/ር መስፍን ወልደ ማርያም

ጉልበት አራዊት የሚተዳደሩበት ሕግ ነው፤ ሕገ አራዊት የሚባለው አራዊት የሚተዳደሩበት ጉልበት ነው፤ በአራዊት ዓለም ማናቸውም ነገር በጉልበት ያልቃል፤ በሰዎችም መሀከል ጉልበት አድራጊ-ፈጣሪ ሆኖ ጎልቶ ሲወጣ የአእምሮንና የኅሊናን መዳከም ወይም ጭራሹኑ አለመኖር ያመለክታል፤ ጉልበት አለን በማለት፣ ወይም ተመችቶናል በማለት፣ ወይም ጠያቂ የለብንም በማለት የማንኛውንም ሰው ሰብአዊ መብቱንና ሰብአዊ ክብሩን መግፈፍ ሦስት ነገሮችን ያመለክታል፤ አንደኛ ጉልበት እንጂ አእምሮና ኅሊና እንደሌለ፣ ሁለተኛ ጉልበት እንጂ ሕግ እንደማይከበር፣ ሦስተኛ በአንተ ላይ እንዲያደርጉብህ የማትፈልገውን አንተም በሰዎች ላይ አታድርግ የሚለውን ሕግ መጣስን ያሳያል፤ በመጨረሻም፣ ዘግይቶም ቢሆን በራስ ላይ ቅሌትን መጋበዝን ያስከትላል፤ የሌላውን ሰውነት ስናረክስ ሰውነትን በጠቅላላው ማርከሳችን ነው፤ ሰውነትን በጠቅላላው ስናረክስ ራሳችንን ከነጉልበታችን ማርከሳችን ነው፤ ራሳችንን፣ ሰውነታችንን ካረከስን በኋላ ዋጋ የለንም፤ ለራሳችን ዋጋ ከሌለን ለሌለች ሰዎችም ዋጋ አንሰጥም፤ ያኔ ክፉ በሽታ ይይዘናል፤ እግራችን ስር በወደቀ ሰው ስቃይ የምንደሰትና የምንስቅ፣ የምንፈነድቅ እንሆናለን፤ ያን ጊዜ የለየለት በሽተኛ ሆነናል።

ይሄ በሽታ ያቃዣል፤ ከሰው ሁሉ በላይ ያሉ ያስመስላል፤ አግሩ ስር የወደቀው አንድ ሰው የሰው ልጅ በሙሉ ይመስለዋል፤ በሽተኛነቱን ስለማያውቅ በሽታው ከሰው በላይ ያደረገው ይመስለዋል፤ እንዲህ ዓይነቱ በሽተኛ በሕግ አሰከባሪነት ሥራ ውስጥ ሲገባ ሕግ የአንድ ማኅበረሰብ ትምክህትና መከታ በመሆን ፋንታ የበሽተኞች በትር ይሆናል፤ በደርግ ዘመን የአራት ኪሎው ግርማ የሠራውን እናውቃለን፤ ዛሬ ደግሞ ልዩ ግርማዎች አሉ፤ መልካቸውን ከካሜራው ጀርባ ደብቀው በሰው ስቃይና አበሳ በሳቅ እየተንከተከቱ ጀብዱዋቸውን በቴሌቪዥን የሚደረድሩ ጀግኖች መጥተዋል፤ መሣሪያ ይዞ መሣሪያ ባልያዘ ሰው ላይ ጀግና መስሎ ለመታየት የሚሠራው ጨዋታ ራስን ክፉኛ ከማጋለጥ በቀር ሌላ ፋይዳ የለውም።

በኢትዮጵያዊ ሰውነት ላይ ማናቸውንም ከሕግና ከሰብአዊነት ውጭ የሆነ ሙከራ ለማድረግ የውጭ አገር ሰዎች ዕድሉን ይፈልጉት ይሆናል፤ ለነሱ ሰዎች ስላልሆን ሰብአዊነት አይሰማቸውም፤ ከአገራቸው ሕግም ውጭ በመሆናቸው በሕግ አይገዙም፤ ዋናው ውጤት ግን ለኢትዮጵያ ሕግ አስከባሪዎች የሚያስተምሩት ግዴለሽነት ነው፤ መታሰር በብዙ ምክንያቶች ይመጣል፤ ስለዚህ በሠለጠነው ዓለም የተለያዩ እስረኞች በተለያየ ሁኔታ ይጠበቃሉ፤ አንዳንዶቹ እንዲያውም በቤታቸው ውስጥ እየተጠበቁ ይቆያሉ፤ ኢትዮጵያ በራስዋ ሥልጣኔ በምትተዳደርበት ዘመን መሳፍንትና መኳንንት የሚታሰሩት በወርቅ ወይም በብር ሰንሰለት ነበር፤ ግዞትም፣ የቁም እስርም ነበር፤ ዛሬ በኢትዮጵያ ውስጥ እስረኞች ሁሉ እኩል ናቸው፤ በቃሊቲ ለየት ያለ አያያዝ የሚታየው ለሙስና ወንጀል ተጠርጣሪዎች ብቻ ነው።

ጉልበትን በጉልበት እቋቋማለሁ የሚል ሰው ሲሸነፍ አያስደንቅም፤ አዲስም አይደለም፤በአለፉት አርባ ዓመታት እየተሸነፉ ከትግሉ ሜዳ ወጥተው በተለያዩ የምዕራባውያን አገሮች የሙጢኝ ብለው የተቀመጡ አሉ፤ በተባበሩት መንግሥታት ደንብ የሙጢኝ ማለት መብት ነው፤ ይህንን መብት መጣስ የመንግሥተ ሰማያትን በር መድፈር ነው፤ በጎንደር የአደባባይ ኢየሱስን ቤተ ክርስቲያን በር መድፈር ነው፤ በአዲስ አበባ የቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያንን በር መድፈር ነው፤ በአዲስ አበባ የአንዋር መስጊድን በር መድፈር ነው፤ ወደመሬት ስንወርድም የሙጢኝ የተባለው አገርን መንግሥት መድፈር ነው፤ የተባበሩት መንግሥታት ደንብን መጣስ ነው፤ ለነገሩ የመንግሥተ ሰማያትን በር መድፈር ከተቻለ ሌላው ምን ያቅታል!

የሙጢኝ ያለን ሰው በአፈና መያዝና ወደአገር ማስገባት አንድ ችግር ነው፤ ይህ የጉልበተኛነት መገለጫው ነው፤ ሁለተኛው ችግር የተያዘው ሰው መብቱና ክብሩ ሳይጓደልበት ማስረጃዎችን ሰብስቦ ለነጻ ፍርድ ቤት አለማቅረቡ ነው፤ በቴሌቪዥን እንደታየው አካላዊ ጉዳት እንደደረሰበት ባይታወቅም፣ ጥልቅ መንፈሳዊ ጉዳት እንደደረሰበት ይታያል፤ በብዙ አገሮች ሕጎች አንድ ሰው ራሱን እንዲወነጅል አይገደድም፤ ሕጋዊ ምርመራም በቴሌቪዥን በአደባባይ አይካሄድም።

ስለዚህም በተጠርጣሪው ላይ የተደረገው ሁሉ ሕጋዊ አይደለም፤ በነጻ ፍርድ ቤት ቢቀርብም በቴሌቪዥን የተናገረው ሁሉ ቢያስታውሰውም በማስረጃነት የሚያገለግል አይመስለኝም፤ ስለዚህም ከጥቅሙ ጉዳቱ ይበልጣል።

ከአፍሪካ አህጉር ወጥቶ የቀይ ባሕርን አቋርጦ አንድ ሰው፣ ገና ወደፊት ክፉ ሊሠራ ይችላል በሚል ሂሳብ በጉልበት አፍኖ ማምጣት የብዙ ነፍሶች ዕዳን ተሸክመው በኢጣልያ ኤምባሲ የሙጢኝ ብለው ተደላድለው የተቀመጡትን የደርግ አባሎች ማስታወስ ግዴታ ይሆናል፤ አድርጋችኋል የተባሉትን ሰዎች የሙጢኝ የማለት መብት አክብሮ አስበሃል የተባለውን ሰው የሙጢኝ የማለት መብት መጣስ ከጥቅሙ ጉዳቱ ይበልጣል።

ከፖሊቲካና ከምናምኑ፣ ጉልበተኛነትንም ከማረጋገጡ በላይ ሌላ ትልቅ ነገር አለ፤ አገር የሚባል ነገር አለ፤ ይህ በአንድ ግለሰብ ላይ የተገኘ ጊዜያዊ ድል የአገርን ከብር የሚያጎድፍና የሚያቀል ይሆናል፤ የአንድ አገርን የመንግሥት ሥልጣን የያዘ አካል አንድ ግለሰብን በአደባባይ ከሕግ ውጭ ለማጥቃት ሲሞክር የራሱን ክብር ዝቅ ያደረግበታል፤ ስለዚህም ከጥቅሙ ጉዳቱ ይበልጣል።

በእኔ ዕድሜ ሰው በአደባባይ ሲገረፍ አይቻለሁ፤ ሰው ተሰቅሎ አይቻለሁ፤ የዚያን ዘመን የእውቀት ደረጃ የዚያን ዘመን የሰው ልጆች የመንፈስ እድገት ደረጃ ያመለክታል፤ የእውቀትም የመንፈስም ደረጃ በጣም ዝቅተኛ ነበረ ማለት ነው፤ ስለዚህም ይህንን ያደረጉትን ዛሬ አንወቅሳቸውም ይሆናል፤ የታሪካችን ጉድፍ መሆኑን ግን ልንፍቀው አንችልም፤ ስለዚህም ሌላ ጉድፍ እየጨመርንበት ታሪካችንን ማቆሸሹ ከጥቅሙ ይልቅ ጉዳቱ ይበልጣል።

ቅጣት በሕግና በሥርዓት ይደረግ ማለት ያጠፋ ሰው አይቀጣ ማለት አይደለም፤ ነገር ግን ምንም አቅም የሌለውን ሰው ይዞ በአደባባይ ማሰቃየትና ማዋረድ አገርንና ሕዝብን ማዋረድ ነው፤ የሰብአዊነትንም የሕጋዊነትንም ሚዛኖች ይሰባብራል።


በሀገሪቱ የስራ ማቆም አድማ እና የተማሪዎች አመጽ ያሰጋል ።

0
0

ወያኔ እስካሁን ድረስ የግንቦት ሰባት የሃገር ቤት መዋቅር በፍጹም እጇ ላይ እንዳልገባ ተረጋግጧል።

Minilik Salsawi (ምንሊክ ሳልሳዊ)


ከመጭው ምርጫ በፊት በኢትዮጵያ ውስጥ የስራ ማቆም አድማ እና የተማሪዎች አመጽ እንደሚያሰጋ ለጠቅላይ ሚኒስትሩ የደህንነት አማካሪ ለሕወሓቱ አለቃ ጸጋይ አርብ እለት የቀረበው ሪፖርት መግለጹን ምንጮች ጠቁመዋል። ምንጮቹ እንዳሉት በወያኔ ውስጥ ስልጣኔን አጣለሁ እፈረካከሳለሁ የሚለው ከፍተኛ ሽብር የፈጠረው ፍራቻ እየተባባሰ መሄዱን እና…
 ወያኔ ለመጭው አርባ አመታት እቆያለሁ የሚለውን ሃሳቡን ሊያኮላሽብኝ ይችላል ያለውን ሁሉ እርምጃ ቢወስድ ምንም አይነት ውጤት እንደማያገኝ እና በይበልጥ ጥላቻ እያሰፋ እንደሚመጣ በተሰበሰበው የመረጃ ሪፖርት ተገልጿል ።

የተቃዋሚ የፖለቲካ ድርጅቶች የሚያስተባብሩ ከሆነ ሕዝቡ የሚከፈለውን መስእዋትነት ለመክፈል ወደኋላ የማይል መሆኑን የጠቆመው ሪፖርት የከተማው የተማረውም ያልተማረውም ሕብረተሰብ በወያኔ ላይ ከፍተኛ ጥላቻ ስላለው ለመጭው ጊዜ ከፍተኛ የሆነ የስራ ማቆም አድማ እና የተማሪዎች አመጽ ያሰጋል ሲል ሪፖርቱ ተናግሯል። እንደ ምንጮቹ አገላለጽ ክሆነ የሃገር ቤት ፓርቲዎች በተለይ ሰማያዊ እና መኢአድ ይህንን እንቅስቃሴ ያስተባብራሉ የሚል የሕዝቡንም አትኩሮት መሳብ እንደቻሉ ሲታወቅ አንድነት እና መድረክ ፓርቲ ውስጥ ያሉ እና ያሰጋሉ የሚባሉ መዋቅሮችን በቁጥጥር ስር ለማዋል ጥረቱ መቀጠሉን ሪፖርቱ አውስቷል።

በወያኔ አስተዳደር እና ባልተማሩ ባለስልጣናቱ እንዲሁም ክድሬዎቹ ሕዝቡ እየተማረረ እንደሆነ እና መንግስታዊው ውሸትና ወመኔነት፣ ሙስና ከፈጠረው የኑሮ ድቀት ጋር ተደማምሮ መጨው ጊዜ ለወያኔ ገሃነም እንደሆነበት በግልጽ የተቀመጠ ሲሆን አብዛኛው የገዢው ፓርቲ አባላት ሳይቀሩ በድርጅቱ ሁኔታ እና ኢዲሞክራሲያዊነት እንደማይደሰቱ እንዲሁም ሕዝቡ እያገለላቸው ሲሆን የሚቀርባቸዉም ሕዝብ ከአንገት በላይ መሆኑን እየገለጹ ስለሆነ የድርጅቱን መኖር እንደማይፈልጉ ታውቋል። አንዳንድ አባላቱ ድርጅቱን ከደርግ ኢሰፓ ጋር እንደሚያመሳስሉት እና በ97 ምርጫ የወሰዱትን እርምጃ በገዢው ፓርቲ በሆነው ድርጅታቸው ላይ ሊወስዱ ይችላሉ ሲል ሪፖርቱ አስቀምጧል።

ከዚህ ጋር በተያያዘ ወያኔ እስካሁን ድረስ የግንቦት ሰባት የሃገር ቤት መዋቅር በፍጹም እጇ ላይ እንዳልገባ ተረጋግጧል። የደህንነት አካላቶች ባደረጉት ማጣራት ግንቦት ሰባት ብለው የተጠቆሙት በራሳቸው መዋቅር ውስጥ ያሉ እና የሃገር ቤት ተቃዋሚዎችን እንዲሰልሉ የተላኩ የገዢው ፓርቲ አባሎች ሆነው ማግኘታቸው ጭራሽ ኢሕአዴግን ውዝግብ ውስጥ እንደከተተው ታውቋል። ከኢሕአዴግ ጽ/ቤት ለደህንነት ቢሮ የተላከው መረጃ እንደሚጠቁመው የግንቦት ሰባት አባልነት የተባሉት አብዛኛዎቹ ለድርጅቱ ጠቃሚ መረጃ የሚያመጡ ሰዎች ሲሆኑ ስለ ግንቦት ሰባት ግን ምንም መረጃ ያላመጡ እና የሚያውቁት ነገር እንደሌለ ይገልጻል።

ወያኔ ምንም አይነት የግንቦት ሰባት መዋቅር ፍንጭ አለማግኘቱ ጭንቀት ውስጥ ስለከተተው በእስር ቤት ያጎራቸውን ወጣቶች በግንቦት ሰባት ዙሪያ ስለላ እንዲሰሩ እና ክትትል እንዲያደርጉ ማሰልጠን ቢፈልግም የመለመላቸው ወጣቶች ፈቅደኛ ሊሆኑለት እንዳልቻሉ ታውቋል፡፤ በቅርቡ እንደተፈታ የሚናገር አንድ ወጣት የላከው መረጃ እንደሚያሳየው የፈለገውን ገንዘብ እንደሚስጡት እና የፈለገው አገር እንደሚልኩት በመግለጽ አብሯቸው እንዲሰራ እና የግንቦት ሰባትን እንቅስቃሴ ተከታትሎ መረጃ እንዲያቀብላቸው ቢያስገድዱት በፍጹም አለመስማማት እንደተለያቸው ተናግሯል። አስተያየት ሰጪዎች ወያኔ ስልጣንን ለማቆየት በሚያደርገው ጥረት የተለያዩ የስለላ መረቦችን እንደሚዘረጋና ተቃዋሚዎች ከዚህ እንዲጠነቀቁ እንዲሁም ተመሳስለው ከሚመጡ ሰርጎ ገቦች ራሳቸውን በመጠበቅ የየፓርቲያቸውን የደህንነት ክፍል እንዲያጠናክሩ አሳስበዋል።

#ምንሊክስልሳዊ

news

Hiber Radio: ግብጽና ኢትዮጵያ ወታደራዊ ጡንቻቸውን እያፈረጠሙ ነው፤ ከአንዳርጋቸው መታሰር በኋላ በየኬላው ፍተሻው ተጠናክሯል

0
0

ጋዜጠኛ ሃብታሙ አሰፋ

ጋዜጠኛ ሃብታሙ አሰፋ


የህብር ሬዲዮ ነሐሴ 18 ቀን 2006 ፕሮግራም

<... ...>

ጋዜጠኛ ቶማስ አያሌው የአፍሮ ታይምስ ማኔጂንግ ዳይሬክተር ሰሞኑን በስደት ካለበት ለህብር ሬዲዮ በአገዛዙ የተወሰደባቸውን እርምጃ በማስመልከት ካደረግንለት ቃለ መጠይቅ

(ሙሉውን ያዳምጡት)

>

ጋዜጠኛ ዳንኤል ድርሻ የሎሚ መጽሔት ሚዲያ ዳይሬክተርና በፖለቲካ ጉዳዮች የምታተኩረው አዲሷ ላሊበላ መጽሔት አሳታሚ ሰሞኑን በስደት ካለበት ከሰጠን ቃለ መጠይቅ (ሙሉውን ያዳምጡት)

>

የህብር ሬዲዮ ጥሪ

ነጻ ፕሬሱና የአገዛዙ የማያቋርጥ ጡጫ (ልዩ ዘገባ )

በአሜሪካ ሚዙሪ ግዛት ፈርጉሰነን ላይ በፖሊስ የተገደለው ጥቁር አሜሪካዊ ወጣት የ ኝተር ስርዓት ነገ ይካሄዳል ። አሜሪካና ያልተቋረጠው የዘር ፖለቲካ (ሁለተኛ ክፍል ልዩ ጥንቅር)

በቬጋስ የኢትዮጵያዊነት ቀን በመጪው ወር ይከበራል በይድነቃቸው ተሰማና በጋዜጠኛ ሰለሞን ተሰማ ስም ውድድሮች ተዘጋጅተዋል(ልዩ ዘገባ)

የግንቦት ሰባት ሕዝባዊ ስብሰባ ጥሪና የአዘጋጆቹ መልዕክት(ቃለ መጠይቅ)

የስነ ልቦና ችግር የሆነው ጭንቀት እና የኢትዮጵአውያን ጥረት(ክፍል አንድ ውይይት)

ዜናዎቻችን

ግብጽና ኢትዮጵያ ወታደራዊ ጡንቻቸውን እያፈረጠሙ ነው

በሰሜን ኢትዮጵያ ከአቶ አንዳርጋቸው መታፈን በሁዋላ በርካታ ኬላዎች ቆመው ፍተሻው ተጠናክሯል

የህዝቡ የመንቀሳቀስ መብት እየተገደበ ነው

መኢአድ ከአራት ዓመት በፊት ከድርጅቱ የተባረሩ አባሎቹ ከገዢው ፓርቲ የደህንነትና ከምርጫ ቦርድ ጋር ተልዕኮ ይዘው ፓርቲ ለማፍረስ እየተንቀሳቀሱ መሆኑን ገለጸ

ኢ/ር ግዛቸው ቀድሞ በዶ/ር ነጋሶ > ተብለው ከፓርቲው የተባረሩን ግለሰብ በአዲሱ ካቢኔያቸው ተቀዳሚ ም/ፕሬዝዳንት አድርገው አሾሙ

ከአንድነት ውህደት የሚያደናቅፈውን ውሳኔ ተቃውመው ከካቢኔ ራሳቸውን ባገለሉት ምትክ አዲስ አባላት መረጠ

በቅርቡ የተሰደዱት ጋዜጠኞች ዛሬም የደህንነት ስጋት እንዳለባቸው ገለጹ

የሕዝቡ ድጋፍ ያስፈልጋቸዋል ተባለ

ሌሎችም ዜናዎች አሉ

የስደት እፍታ –ፋሲል አየር ወለድ (ማትያስ ከተማ- ወለላዬ ከስዊድን)

0
0

(አጭር ልብወለድ)
 ማትያስ ከተማ (ወለላዬ ከስዊድን)

እግሬ እንደተነፋች ዶሮ ጢል ብሎ አብጧል። ጫማዬን ወጥሮት ማቆም እያቃተኝ ነው። ይኼን አሳዛኝ ሁኔታ ኃላፊው ማወቅ አለበት። ሄድኹኝ ምንም ሳልናገር ጫማዬን አውልቄ አሳየሁት። እሱም ምንም ሳይናገር ወደ ጓዳ ገብቶ ተመለሰ። የፕላስቲክ ነጠላ ጫማ አንጠልጥሏል።

ጥርስ ያልነቀለበት

እትብቱ ዘመዱ ያልተቀበረበት

ባዕድ መሬት ባዕድ

ዓይኑ ውሃ ኹኖ ቦታው ጭጋግ ለብሶ 

ባሳብ እየዋኘ ሄደ ተመልሶ 

አገሩ ናፈቀው 

አሁን ይህን ጊዜ ዓደይ አበባ ነው

ደማቅ ሰማያዊ ወሩ መስከረም ነው

አጭር ነበር ጉዞው የሄደው ባሳቡ

ወዲያው ተመለሰ 

ተመለሰ 

ዓይኑ እምባ አቀረረ። 

(ግጥም ገብረክርስቶስ ደስታ)

ስደት ከወጣሁ ሦስት ወራት አልፎኛል። በቀጥታ የገባሁት ወንድሜ ቤት ነበር። ሚስትና ሁለት ህጻናት ልጆች አሉት። ሆኖም የራሴ የሆነ አንድ መኝታ ክፍል አላጣሁም። ተዋበ በፊት የማውቀውን አይነት ሆኖ አላገኘሁትም። ሳቁ ደርቋል፣ አጫጭር ነገሮች ተናጋሪ ሆኗል። ነገሮች የሰለቹት አይነት ነው። ሊያውራ የጀመረውን እንኳን አይጨርሰውም። በእንጥልጥል እያለ ወደሌላ ይሸጋገራል። የሌላን ሰው ንግግር የሚሰማው ከፊሉን ነው። የገባው ስለሚመስለው አይፈልገውም፤ የአስራ ሁለት ዓመት የውጪ ቆይታው ብዙ ለውጦታል።

አመሉ ባይገባኝም አብረን መኖር ጀምረናል። ሚስቱ የሚገባኝን አክብሮት አልነፈገችኝም። ብዙ ጊዜ መንፈሣዊ መዝሙር ታዳምጣለች። ስለኖረችበት አካባቢና ስለቤተክርስቲያን ማውራት ያስደስታታል። በጨዋታ ማኻል በነገር ነደፍ ማድረግ ትወዳለች። ያም ሆኖ ብዙ የምታውከኝ ሴት አልነበረችም።

እነሱጋ በገባሁ ሦስተኛ ወር ተዋበ ሥራ አገኘልኝ። አያይዦ ምክሩን ያዥጎደጉደው ጀመር። “ስማ ማንንም ማመን አይገባህም። ሰው አገኘሁ ብለህ የልብህን ሁሉ አትዘርግፍ። የሥራ ሰዓትህን አክብር። ቀድመህ ግባ፣ ስትወጣም ሰዓቱን ጠብቀህ ውጣ። መጠጥ የሚባል አካባቢ እንዳትደርስ እዛ የጋፍከው ይበቃሀል …

በጥሞና አዳመጥኩት። አጉል እንደ አባት፣ እንደ አባት የሚያደርገው ቢያናድደኝም ከማድመጥ ውጪ ዕድል አልነበረኝም፣ ምክሩን አቋርጦ ሲያየኝ ከቆየ በኋላ “ተግባባን!?” አለኝ። “አዎን! ተግባብተናል፤ ግን የቋንቋውን ነገር እንዴት አደርጋለሁ? ማለቴ ሥራ ላይ …

“ስለቋንቋው አታስብ እያደር ትለምዳለህ። አንዳንድ የምትሰማቸውን ቃላቶች ለመያዝ ሞክር። ደግሞም በሥራው ጎበዝ ከሆክና ከሠራኽላቸው ስለቋንቋህ አይጨነቁም፣ በንግሊዘኛም መግባባት ትችላለህ።” በማግስቱ ወስዶ አገናኘኝ። ሥራው ላውንደሪ ውስጥ ነው። የሆቴሎችና የመሰል ድርጅቶች አንሶላ፣ ፎጣ፣ ብርድ ልብስ፣ ትራስ ልብስ፣ እና የመሳሰሉት ይታጠባሉ። የከተማው ልብስ ሁሉ የመጣ ይመስል፣ ቤቱ በልብስ ተጨናንቋል።

አሰሪው ወዲያውኑ እንደደረስኩ ከአንድ ሰው ጋር አቆራኝቶ ሥራውን አስጀመረኝ። የታጠበ አንሶላ ከጋሪ ላይ እያነሱ ጠረጴዛ ላይ መዘረር ያዝን። አንድ ጋሪ ጨረስን፣ ሌላ ተተካ፤ ያ ሲያልቅ ሌላ ቀጠለ፤ አንሶላውን ስንጨርስ ፎጣ ቀጠለ፤ ፎጣ ሲያልቅ ብርድ ልብሶች ታጥበው መጡ። ትራስ ልብስ ሌላም ሌላም የማያልቅ ሥራ፣ እየተጨመረ የሚሄድ ሙቀት ነፍሴ በአፍንጫዬ ልትወጣ ምንም አልቀራት። የተጠንጠለጠለውን የግርግዳ ሰዓት አየሁት፣ የፈጣሪ ያለህ ገና ለመውጣት ሙሉ ሰባት ሰዓት ይቀረኛል። አልጋ ላይ ተኝቶ ሞቱን እንደሚጠባበቅ በሽተኛ በፍራቻ ተዋጥኹ። አብሮኝ የሚሠራው በከፍተኛ ድምጽ አንባረቀብኝ። ሌላ እያሰብኩ ሥራው ላይ እንደደከምኩ የገባኝ በኋላ ነው።

እንደገና አንሶላ ተጀምሯል። ይበልጥ እየተጣደፍን መሥራት ጀመርን። ኾኖም አሰሪው አልረካብኝም፤ ወደኔ ሲንደረደር መጣ።

“እንግሊዝኛ ትችላለህ?”

“አዎን!” ተቅለሰለስኩ።

“በፍጥነት መሥራት ይገባሃል።” ከኔ አጣማጅ ጋር በሚያስደነግጥ ፍጥነት አንሶላውን እየዘረጋ አሳየኝ። ወይ ጣጣዬ እንዴት አድርጌ ነው እንደዚህ የምሠራው። በላብ በተጨማለቀው ፌቴ ላይ እንባዬ ፈሰሰ። ማንም ልብ ያለው የለም። አሰሪው እኔን አያይዞ ወደሌሎቹ ተፈተለከ።

እየተጣደፍኩ በመሥራት ላይ ነኝ። እናቴ እፊቴ መጣች “ሰው እንዴት የተኛበትን ማንጠፍ ያቅተዋል? የበላኽበትንስ ብታነሳው ምናለ? ተው! ልጄ ግፍ ይሆንብኻል”። በደንብ! እናቴ፣ ይኼው ግፉን አገኘሁት … ይቅር በይኝ። ጉሮሮዬ ላይ አንድ ነገር መጥቶ ተወተፈ። እናቴ ገጽታዋ እንደጠቆረ ፊቷን አዞረችብኝ። “ብዬህ አልነበር …

አባቴ ተራውን መጣ ነጭ ሸሚዝ ለብሷል። “ስማ አንተ! ይሄን ሸሚዝህን ብታጥበው ምናለ። ካልሲህን አውልቀህ በየስርቻው የምትወትፈው ህጻን ልጅ መሆንህ ነው? ብቻ መጨረሻህን አይቼ …”፤ አባቴ ይኼው መጨረሻዬ ይቅር በለኝ። ድምጼን ከፍ አድርጌ ይቀር በለኝ ስል ተሰማሁ። አብሮኝ የሚሠራው የተቆጣሁ መስሎት ሲያየኝ ከቆየ በኋላ ወደ አሰሪው ሄደ።

አሰሪው ወደኔ ሲመጣ ጊዜ አልፈጀበትም። እጄን ይዞ እየመራ ወደሌላ ቦታ ወሰደኝ። ፎጣ ለየብቻ የሚታጠፍበት ቦታ ነው። በትልቅ የፕላስቲክ ሙሉ ጢም ያለ የደረቀ ፎጣ ቀርቧል። የተለያዩ መጠን ያላቸው ፎጣዎች በአራት አይነት መልክ ይታጠፋሉ። በፍጥነት አስተጣጠፉን አሳይቶኝ ሄደ።

ማጠፍ ጀመርኩ ፍጥነት ቢያንሰኝም ሥራው ቀሎኛል። የቀረበልኝን አገባደድኹ ስል ሌላ ቀጠለ፣ እሱን ስጨርስ ሌላ፣ አሁን አቅለሸለሸኝ። ገና ሁለት ሰዓት ይቀረኛል። መቼ ነው የሚያልቅ? ምን አይነት ጉድ ውስጥ ነው የገባሁት? ተዋበ ፌቴ መጥቶ ተወዘፈ። ዛር ያስውበውና እዚህ አምጥቶ የሚጫወትብኝ እሱ ነው። ይሄ ሥራ ኾነና ደሞ ምክሩ በዚህ ላይ “አንተ ደግሞ ሠርተህ ጌድዮንን ታመጣለህ” ይበለኝ?! በስመአብ! …

እግሬ እንደተነፋች ዶሮ ጢል ብሎ አብጧል። ጫማዬን ወጥሮት ማቆም እያቃተኝ ነው። ይኼን አሳዛኝ ሁኔታ ኃላፊው ማወቅ አለበት። ሄድኹኝ ምንም ሳልናገር ጫማዬን አውልቄ አሳየሁት። እሱም ምንም ሳይናገር ወደ ጓዳ ገብቶ ተመለሰ። የፕላስቲክ ነጠላ ጫማ አንጠልጥሏል።

“ምንድነው?”

“ይሄን ቀይረህ ሥራ። ጊዜ አታባክን!”፤ አቋርጨ በመምጣቴ ተበሳጭቷል።

“አልሠራም! እግሬ እንደዚህ ሆኖ አልሠራም።” የራሴ ድምጽ ለራሴው አስደነገጠኝ። ጩኸትና ንዴት የተቀላቀለበት ነበር።

“መሄድ ትችላላህ። አያይዞም ነገም መምጣት አያስፈልግኽም። ለሥራው ብቁ አይደለህም” አለኝ።

* * *

እቤት ስደርስ ተዋበ በሁለት ልጆቹ ተከቦ ሶፋው ላይ ተጎልቷል። ባለቤቱ ማብሰያ ቤት ሳህን በማጣጠብ ላይ ናት። “ጌታው ደህና መጣህ?”

“ምን ጌታው ትለኛለኽ? ባርያው በለኝ” በንዴት መልስ ሰጠኹ።

“ምን ኾነሃል?”

“ምን ኾነሃል ትለኛለህ እንዴ ደግሞ? እየው እስቲ፣ ጫማዬን ወርውሬ እንደፊኛ የተነፋ እግሬን ዓይኑ ስር አስጠጋሁለት። “እየው ይኼን ደግሞ” ሁለተኛውን እግሬን ስቀይር ባለቤቱ መጥታ ነበር። ንዴቴንና ሁኔታዬን ስታይ ክው ብላ ቀረች። ልጆቹ ማልቀስ ጀመሩ። አባታቸውን የምደበድበው ሳይመስላቸው አልቀረም። እናትየው ልጆቹን እያባበለች ወደ መኝታ ቤት ገባች።

ተዋበ የሚናገረው አልነበረውም። የበላይነት ስሜቱ ሲተነፍስ ተመለከትኩ። ኩምሽሽ ብሎ አንገቱን ደፋ አላሳዘነኝም በለው በለው ነበር ያለኝ። ከላይ የለ ከታች የለ ጸጥ እንዳለ ቀረ። እኔ ቀጠልኩ። “ስማ እዚህ ያመጣኸኝ ለባርነት ነው እንዴ? እምበላው አጣሁ አላልኩህም። አሁንም እዚህ አገር በእንዲህ አይነት ኑሮ ህይወቴን ልገፋ አልፈልግም። እዛ ስትመጡ ሰው እየመስላችሁ፣ ጉራችሁን ትነፋላችሁ፤ እዚህ ሲመጣ ባዶ … እኔ እንደውም ድሮ የማውቅህ ተዋበ መሆንህንም እጠራጠራለሁ፣ አንተ ብሎ ተዋበ?! “ጀዘበ” ቢሉህ ይሻል ነበር። እንደጉድ ተንጣጣሁ። ተዋበ ባላሰበው ጊዜ እንደዚህ ባወረድኩት መአት ግራ ተጋብቷል።” ቃል ቢመልስ የበለጠ እንደምቀጥል ገብቶታል፤ ዝም በቃ ዝም …

ሶፋው ላይ እንደተዘረጋሁ እንቅልፍ ወስዶኝ ኖሮ እኩለ ሌሊት ላይ ነቃሁ። ጸጥ ያለ ሌሊት። ጠረጴዛው ላይ ምግብ ተከድኖ ተቀምጧል። ቀስ ብዬ ተነሳሁ እግሬ አሁንም እንዳበጠ ነው። ስነካው ቦታው ስርጉድ ብሎ ቀረ። ስራመድበት እያመመኝ መኝታ ቤት ገብቼ ተጠቀለልኩ።

ጠዋት ስነሳ እረፋዱን አምስት ሰዓት ሆኗል። አቤት! እንዴት ተኝቼ ኖሯል! ምን ተኝቼ ሞቼ ነበር ቢባል ይቀላል። ቤቱ ውስጥ ማንም የለም። ባልና ሚስት ሥራውን ሊሸከሽኩት ሄደዋል። ልጆቹን ከመዋያ ቦታቸው ሲመለሱ እንደሚያመጧቸው አውቃለሁ። እግሬን አየሁት በመጠኑ ጎደል ብሏል።

የማታው ነገር ሳስበው እፍረት ተሰማኝ። የኔ ልፍለፋ፣ የተዋበ ዝምታ፣ የልጆቹ ለቅሶ፣ የሚስቱ ልጆቹን ሰብስቦ መግባት፣ አሳፋሪ ነበር። እፍረት ቢሰማኝም እራሴን ጥፋተኛ ማድረግ አልፈለኩም። ነገሩን ለመርሳት ሞከርኩ ሆኖም ማታ መገናኘት ይኖራል፤ ምን ብዬ ነው ዓይናቸውን የማይ? የራሱ ጉዳይ የመጣው ይምጣ! ረሃብ አፉን ከፍቶ እያላመጠኝ ነው። ማታ የተቀመጠልኝን ምግብ ጥርግ አድርጌ በልቼ ቤቱን ለቅቄ ወጣሁ።

ውጪው ደስ ይላል። ሙቀቱ ኃይለኛ ቢሆንም ከባህሩ የሚነፍሰው ነፋስ አቀዝቅዞታል። ቀዝቃዛውን ንፋስ እየሰነጠኹ ወደባህሩ ተጓዝኩ። መንገድ ላይ የፈረንጅ ባልና ሚስቶች አየሁ። ልጃቸውን በጋሪ አድርገው ይጓዛሉ። ባል ጋሪውን ይገፋል። ቦርሳ አንጠልጥሏል። በሌላ እጁ ትንሽ ሴት ልጅ ይዟል። ሚስት ፊት ለፊት ትሄዳለች ከነሱ ጋር ጉዳይ ያላትም አትመስል። ሰውዬው እመቤቱን የሚከተል እንጂ ከሚስቱ ጋር የሚሄድ አይመስል። አይ! ቁመናዋ ቀጥ ያለ አቋም ሁሉም ሴቶች እንዲሁ ናቸው። ወንዶቹ ናቸው የሚያሳዝኑ በካኒተራና በጅንስ ሱሪ ተጣብቀው ሲጎተቱ ነው የሚውሉት።

ሁሉም ወንድ መጀዘቡን ያየሁት ዛሬ ነው። ሚስቶቻቸው ሳይገርፏቸው አይቀሩም። ተዋበንም ሚስቱ ስትገርፈው ታየኝ። “በናትሽ! በናትሽ! …” ተንበርክኮ ይለምናል።

“ለምን ዕቃውን አላጠብክም?”

“ቸኩዬ ወጥቼ ነው”

“በሁሉም ነገር ነው የሰነፍከው …”

“ሥራው እያደከመኝ ነው።” … ራሴው በፈጠርኩት ምናባዊ ቀልድ በሳቅ ፈረስኩ። ብዙ የጀዘቡ ባሎችን እያሰብኩ ወደ ባህሩ ተጠጋሁ። ባህሩ ግራና ቀኙን በትላልቅ ሆቴሎች ተከቧል። አሸዋማ ሜዳው ላይ በስስ የውስጥ ሱሪና በጡት መያዥያ ብቻ ያሉ ብዙ ሰዎች በላስቲክ አልጋ ፀሐዩ ላይ ተዘርረዋል። ቀርቤ በማየት ላይ ነኝ። በደረታቸው የተኙ ረጃጅም ቀጫጭን ሴቶች፣ ሌሎች ሰፊ የፀሐይ መነጽር ያደረጉ በጀርባቸው የተኙ ሴቶች፣ ቀይ፣ ቢጫ፣ ሰማያዊ፣ ግራጫ፣ ዥንጉርጉር፣ የተለያየ የውስጥ ሱሪ “ስብዐት ለአብ! ምን ይመስላሉ?” ፊት ለፊት ያለው ደረጃ ላይ ተቀመጥኩ። በቅርብ አፍጥጨ እያየሁ ነኝ። ብዙ ግን አልቆየሁም ተነሳሁ። ሁልግዜ እንደዚህ ሆነው ሳያቸው ያመኛል። ምን አስደበቀኝ ህመም አይደለም እናደዳለሁ። ምን መናደድ ብቻ … እናታቸውን ብሽቆች ተነሳሁ፣ የባህሩ ጠርዝ ላይ በቀጭኑ በተዘረጋው መንገድ ቁልቁል መጓዝ ጀመርኩ። ብዙ ሰው ወደዚያ እየተጓዘ ነው ቁምጣ ያለበስኩ እኔ ብቻ ነኝ። ጅንስ ሱሪዬን ቆርጨ ቁምጣ አድርጌ ልለብሰው አስቤ ነበር፤ ግን ፈርቼ ተውኩት። ፈጥሮ ፈጥሮ ፈጣሪ የጡንቻ ስጋ የነሳን መሆናችን አናደደኝ።

እንደወትሮዬ ጥላ ቦታ ፈልጌ የባህሩን ትርዒት ማየት ያዝኩ። እነዛ ህመሞች ከሩቅ ይታያሉ። አሁን ግን ሰው ሳይሆን ሜዳ ላይ የፈሰሱ ፊኛዎች መስለዋል። ትናንሽ የሞተር ጀልባዎች ባህሩን እየሰነጠቁ ያልፋሉ። ትልቅ መርከብ በባህሩ ጥግ በኩል የሰመጠ ህንጻ መስሎ ተገሽሯል። መናፈሻው ላይ አልፈው አልፈው ከመሬት ተቸክለው በተሰሩት አግዳሚዎች ላይ ሴቶችና ወንዶች በጥንድ በጥንድ ተቀምጠዋል። አይስክሬም የሚልሱ፣ ከንፈር ለከንፈር የሚላላሱም አሉ።

ይሄን የመሳሰለው ነገር ባለፉት ሦስት ወራቶች በተደጋጋሚ ያየሁት ነው። ዛሬ ግን አንድ አዲስ ሁኔታ ተፈጠረ። ከቀኜ በኩል ባለው የባህር ጠርዝ አንድ ኢትዮጵያዊት እየመጣች ነው። በርግጥ ከሷም በፊት ሌሎች ኢትዮጵያውያን አይቻለሁ። አንዳንዶቹ አፍጠው እያዩኝ ሰላም ልላቸው ስል ፊታቸውን ያዞራሉ። የቁጣ ያህል ባንገታቸው ሰላምታ ሰጥተውኝ የሚያልፉም አሉ። ከሩቅ አይተው እንዳላየ የሚሄዱም ብዙ ናቸው። ያም ሆኖ አብዛኛዎቹን በዓይን አውቄአቸዋለኹ። የምትመጣዋ ሴት ግን አዲስ ናት። ከሴት ጋር ቁጭ ብዬ ያሳለፍኩት ጊዜ ዘመናት ያለፉት መስሎ ተሰማኝ። ድምጻቸው፣ ሳቃቸው፣ ኩርፊያቸው፣ ጠረናቸው እንደጉድ ናፍቆኛል።

ኢትዮጵያዊቷ እየቀረበችኝ መጣች። ስስ ሸሚዝና ከግሩ ሰብሰብ ያለ ቀላል ሱሪ ለብሳለች። ጠይም ሰልከክ ያለፊት፣ በግዴለሽነት የተያዘ ረጅም ጸጉር አላት። በላዩ ላይ ኮፍያ ደፍታለች። ደፍረስ ያሉ ዓይኖቿ ደስ ይላሉ። ከላይ ቀጥ ብሎ ወርዶ ማኽሉ ላይ ከፍ ያለው አፍንጫዋ ማንነቷን አክብዶት ስጋት ላይ ይጥላል። አቤት በራስ መተማመን እየተጀነነች ጎኔ ደረሰች። ብለክፋት ምን ታመጣለች? ምንም ይሄን ከማለቴ አፌ ቀደመኝ።

“ሄይ! ጠጅቱ ሰላም ነሽ?”

ፊቷን ወደኔ አዙራ አትኩራ ካየችኝ በኋላ “እኔን ነው?” አለች አፍንጫዋን ወደላይ እየፈነነችው።

“አዎን! ጠጅቱ አይደለሽ እንዴ?” ደንግጫለሁ የተሳሳትኩ ለመምሰል ጣርኩ። ድንጋጤዬን አውቃለች። ይበልጥ ተጠጋችኝ። ጆሮዬን ይዛ ሽቅብ ልታነሳኝ መሰለኝ። ወይ መዋረድ!

“ለመሆኑ የማናት ጠጅቱ?”

“አብረን የተማርን … ማለቴ የሰፈራችን ልጅ” ዕድሜዋን ስገምት ከኔ ጋር ልትማር የምትችል አይደለችም።

“ስማ! እዚህ ተቀምጠህ ጠጅቱ፣ ሻሽቱ እያልክ ሴት ከምትለክፍ ለምን ሥራ አትሠራም። አገር ቤት አደረከው እንዴ? የኛ አራዳ ባንተ ቤት መጠበሱ ነው። ስድ ካንተ የባስኩ ጨላጣ የመነን ተማሪ ነበርኩ”

“መንን!” አፌን ይዤ አያት ጀመር።

“አዎ! መነን፤ ምኑ ነው ያስገረመህ?”

“አይ የናቴን ስም ስትጠሪ ደንግጨ ነው።” ዋሸሁ።

“አትዋሽ! አሮጊት ናት ማለትህ ነው። ለማንኛውም ዕድሜዬንም ቢሆን ሰርቼበታለሁ።” እማታፈናፍን ሴት ሆነችብኝ። ይባስ ብላ ጎኔ ተቀምጣ በጥያቄ ታጣድፈኝ ጀመር።

”መቼ ነው የመጣኸው?”

“ሦስት ወራት አለፈኝ።” ፖሊስ የሚጠይቀኝ ይመስል ትክክለኛ ቃሌን በመስጠት ላይ ነኝ።

”ከየት ነው የመጣኸው?”

ኮስተር አልኩ “ከኢትዮጵያ ነዋ!”

”የአዲስ አበባ ልጅ ነህ?” አንገቴን ነቅንቄ አረጋገጥኩ።

”እኔም ያዲስ አበባ ልጅ ነኝ” ሳቅ አለች።

“ግን አትመስይም” ላበሽቃት ፈለኩ።

“እንዴት?”

“ሀርድ ትሰጫለሽ፣ ትቆጫለሽ፣ ምናምን አለ አይደል” … መሳቅ ጀመረች። ስትስቅ ደስ ትላለች። ያ ሁሉ ክብደቷ በኖ ጠፋ። የቤተሰብ ያህል የሚቀርቧት ሆና ተገኘች።

”ለመሆኑ ከመጣህ ሥራ ሠርተህ ታውቃለህ?”

“ሠርቼ ነበር”

”ታዲያ ለምን ተውከው?” ምንም አልተናገርኩ ጫማዬን አውልቄ እግሬን አሳየኋት።

”ምን ሆነህ ነው?” የትናንት ውሎዬን አንድም ሳላስቀር ነገርኳት፣ ከውስጤ አውጥቼ የጣልኩት ያህል ነበር ቀለል ያለኝ።

ቃል ሳትተነፍስ ካዳመጠችኝ በኋላ፣ ስለራሷ ማውራት ጀመች። እንደመጣች ሆቴል ተቀጥራ ትሠራ እንደነበር። ድስት ስታጥብ ኬሚካሉ የሁለት እጆቿን ቆዳ ቀፎ እንዳነሳው። አልጋ ማንጠፍ ጀምራ ወገቧን ሰባብሮ እንደጣላት። ሽማግሌና አሮጊቶችን መርዳት ተቀጥራ ሳይሆንላት እንደቀረ። የቢሮ ጽዳት ገብታ ያጋጠማትን አንድም ሳታስቀር ዘክዝካ ነገረችኝ። ይህን ስታወራ ዓይኖቿ በእንባ ረጥበው ነበር፤ የሚያስለቅሳት ግን ያ ብቻ አልነበረም፤ አያይዛ እንዲህ አለችኝ፤ “በዛው ወቅት እናቴ ሞተችብኝ፣ ችግሬን እማዋየው ኀዘኔን እማካፍለው ማንም አልነበረም፣ ባህር አጠገብ ብቻዬን እየሄድኩ አለቅስ ነበር።” እንባዋ እንደገና ፊቷን ሞላው። ምን ብዬ እንደማጽናናት ላውቅ አልቻልኩም፣ እንባዬ ግን ከሷ ባልተናነሰ ሁኔታ ይፈስ ጀመር። በራሴ ብሶት የፈሰሰው እንባዬ በልቧ ውስጥ ትልቅ ስፍራ መያዙን ያውኩት ግን በኋላ ነበር።

በዝምታ ባህሩ ላይ እንዳፈጠጥን ብዙ ቆየን። ከብዙ ዝምታ በኋላ፤ እዚህ ከተማ ነው የምትኖሪው? ብዬ በመጠየቅ ዝምታውን ገፈፍኩት።

“አይደለም! ከዚህ አራት ሰዓት የሚያስኬድ ቦታ ነው ያለሁት። ከባለቤቴና ከልጆቼ ጋር ለሦስት ቀናት እረፍት ነበር የመጣነው። እነሱ ክፍል ሲገቡ እኔ ባህሩን ለማየት መጣሁ። ነገ በጠዋት እንመለሳለን። ለመሆኑ እዚህ ዘመድ አለህ?”

“አዎን! ወንድሜ አለ”

”እሱጋ ነው ያረፍከው?”

“ሌላማ የት እገባለሁ ብለሽ?”

”ይሄውልህ እኛ ባለንበት ከተማ ባለቤቴ በበላይነት የሚመራው ድርጅት አለን። ድርጅቱን በቅርቡ ልናስፋፋው አስበናል። በዛን ጊዜ እኛጋ ሥራ የማግኘት ዕድል ይኖርኻል፣ ብዬ እገምታለሁ። ሥራውም ከነገርከኝ ሥራ መሻሉ አይቀርም። ወንድምህ ከዚህ በመራቅህ የሚከፋ አይመስለኝም። አንተስ ሥራው ቢገኝ መምጣት ትፈልጋለህ?” ብላ ጠየቀችኝ።

“እንዴ! ሥራ ተገኝቶ ነው! የትስ ቢሆን ምን ቸገረኝ። ልሠራ አይደል እንዴ የመጣሁት።” ቀልጠፍ ብዬ መልስ ሰጠሁ። ከትንሽ ቦርሳዋ ውስጥ ካርድ አውጥታ ሰጠችኝ። የድርጅቱ ስም አድራሻውና የስልክ ቁጥር ሰፍሮበታል፣ ከላይ ኤልሳበጥ ካሳዬ ጀነራል ማናጀር የሚል ስም በወርቃማ ቀለም ሰፍሯል። “በዚህ ስልክ ደውል፣ ማናት ቅድም ያልካት ጠጅቱ ነው ምናምን ሳልሆን ኤልሳቤጥ ካሳዬ ነኝ።” ትስቅ ጀመር።

የተቀጠርኩ ያህል ብድግ ብዬ ምስጋና አቀረብኩ። ለሷ ያለኝ አክብሮት ገና በፊት ሰማይ ጥግ ደርሶ ነበር። ለቅድሙ ለከፋ ግን ይቅርታ መጠየቅ አላስፈለገኝም። ”ምንም ችግር የለም ደውል የወንድምህንም ስልክ ብትሰጠኝ ጥሩ ነው አለች”። በብጣሽ ወረቀት ጽፌ ለመስጠት አፍታም አልወሰደብኝ። ልትሄድ ተነሳች፤ ያረፉበት ሆቴል መግቢያ ድረስ አብረን ተጓዝን። ልንለያይ ስንል “ምናልባት በሌላ ጉዳይ ከመጣሁ ባህሩን ድጋሚ ልንጎበኘው እንችላለን” አለችኝ።

“አይ! ባህሩጋ ካንቺ ጋር መሂድ አልፈልግም።”

”ለምን? አለች በመገረም።

“ዳግመኛ አብሬሽ ማልቀስ ሳይከብደኝ አይቀርም” አልኳት። በሳቅ እየተንፈረፈረች ወደ ሆቴሉ ገባች። ካርዱን እንደገና አውጥቼ አየሁት። ”ኤልሳቤጥ ካሳዬ – ጀነራል ማናጀር”

* * *

mak

የትናንት ውሎዬንና የዛሬ ገጠመኘን እያሰብኩ ባህሩን ለቅቄ ወደ ከተማው አመራሁ። የሥራ ሰዓት መውጫ በመሆኑ የብዙ ሰዎች እንቅስቃሴ ይታያል። ደስ ደስ የሚሉ ቡና ቤቶች፣ ተደርድረዋል፤ መግባት አማረኝ ኪሴ ያለው ገንዘብ ለቢራ መጠጫ እንደማያንስ አውቃለሁ። ”ሀፒ ሀወር” የሚል የተጻፈበት ቤት ገባሁ። ወንበር አልያዝኩም በቀጥታ ባኮኒው አጠገብ ተጠጋሁ፣ ምን ምን የቢራ አይነት እንዳለ እስከዋጋው ግርግዳው ላይ ተለጥፏል። ረከስ ያለውን አዘዝኩ አብዛኛው የሚጠጣው እሱኑ ነበር። ባለጌው ወንበር ላይ ቂብ ብዬ የቀረበልኝን ድራፍት በአንድ ትንፋሽ አጋመስኩት።

ከመጠጥ መደርደሪያው ከፍ ብሎ በደንብ በተዘጋጀ ሁኔታ የብዙ ሰዎች ፎቶ በምርጥ ፍሬም ተሰቅሏል። ባለጢም፣ ባለፒፓ፣ ወፍራም ቀጭን፣ ወላቃ፣ የሚስቅ፣ የተኮሳተረ የተለያየ መልክ፣ የቴክስ ኮፍያ ያደረገም አለ። አንድ ደግሞ ፎቶ የሌለበት ምርጥ ፍሬም የመሃሉን ቦታ ይዟል። የሃገሩ ታላላቅ ሰዎች ይሆናሉ ብዬ ገመትኩ። ግምቴ ልክ መሆኑን ማረጋገጥ ግን ነበረብኝ። ድራፍቱን አጋብቼ ሁለተኛውን ሳስቀዳ እነዚህ ሰዎች ምንድናቸው? ብዬ ባለቤቱን ጠየኩ።

እንደቀልድ ዞር ብሎ አይቶአቸው ሲያበቃ ”የዚህ ቤት የረጅም ዘመን ምርጥ ጠጪዎች ነበሩ። ዛሬ ሁሉም ተለይተውናል …” እንዳለኝ በርከት ያሉ ሰዎች ስለገቡ ለመታዘዝ ወደነሱ ሄደ። ጎኔ ተቀምጦ መጽሔት ያገላብጥ የነበረው ሰው መጽሔቱን እፊቱ ወርውሮ ወደኔ ዞረ። መደቡ ጥቁር ሆኖ ቀይ መስመር ያለበት ሸሚዝ ለብሷል። እጅጌውን እላይ ድረስ ጠቅልሏል። ቴክስ ሽማግሌ ነው፤ በመጠኑ አይቶኝ ካጠናኝ በኋላ “ሁሉም የዚህ ቤት ደንበኞች ነበሩ። በየተራ አለቁ። ይታይኻል የሞቱበት ዓ.ም. ከስር ተጽፏል።” ያላየሁትን ነገር አሳየኝ። ከሞተ ሃምሳ ዓመት ያለፈው ሁሉ እንዳለ አቀናነስኩ።

ቀጠለ “እነዚህ ፎቷቸው የተገኘ ብቻ ናቸው። አንዳንድ ብኩኖች ደግሞ እነዛውልህ” አለኝ። ባመላከተኝ ጠርዝ ደግሞ ፒፓ፣ ብዕር፣ መነጽር፣ ሻርፕ፣ ላይተር እና ሌሎች እቃዎች በተመሳሳይ ምርጥ ፍሬም ተከተው ተሰቅለዋል። ከስራቸው በወርቅማ ቀለም ስማቸው ተጽፏል። ምንድነው? ለማለት ወደ ሰውዬው ዞርኩ፤ “ጥለው የሄዱት እቃ ነው፣ ሲሞቱ ውለታቸውን የማይረሳው የተከበረው ቡና ቤት እንደዚህ በክብር እንዲቀመጥላቸው ያደርጋል” አለኝ። ራሴን በመነቅነቅ አድናቆቴን ገለጽኩ።

ቴክሱ ማስረዳቱን አላቆመም፣ “ይሄ ክፍቱ ፍሬም ደግሞ መጠጥ እየጋቱ የሚያሰናብቱን ክቡር ሰብሳቢያችን ሲሞቱ ፎቷቸው የሚያርፍበት ቦታ ነው።” በሁለት እጁ ባለቤቱን አመላከተኝ። ጎናችን ያሉ ጨዋታውን የማይሰሙ የመሰሉ ሰዎች ሁሉ ከኔና ከሰውዬው ጋር ይስቁ ጀመር። ሰውዬው አላቆመም፤ “ከባዶው ፍሬም በላይ ያሉት ሦስት መኳንንት ደግሞ እኛን ላሁኑ ባለቤት አደራ ሰጥተው ያለፉ አባትና አያቶቹ ናቸው። ለውለታቸው ክብር ባርሜጣዬን አነሳለሁ።” ያክተር ሳቁን ለቤቱ ለቀቀ። በመጨረሻ ወደኔ ጠጋ ብሎ ሚስጢር እንደሚናገር፤ “ወደፊት እኔም ከነዚህ ክቡር ጓደኖቼ ጎን ቦታ አገኛለሁ የሚል እምነት አለኝ። ይሄንንኑ እምነቴን ለማጠናከር ነው ዛሬም እዚህ የተገኘሁት” ብሎኝ እየሳቀ ድራፍቱን አነሳ። ከዚህ በኋላ እሱ ከሌሎች ሰዎች ጋር በሃገሩ ቋንቋ ወሬውን፤ እኔም የራሴን ሀሳብ እያመነዠኹ ቆየን። በኋላ ግን ወደኔ ዞሮ “ከዬት ሀገር ነው የመጣኸው?” አለኝ።

“ከኢትዮጵያ”

“ኦ! ከኃይለሥላሴ ሀገር ”

“ልክ ነው”

“ስመ ገናና መሪ ነበሩ። እዚህ አገር የመጡ ጊዜ በአካል አይቻቸዋለኹ። ያን ጊዜ ወጣት ነበርኩ። ለኃይለሥላሴ ክብር ለሁለታችን ቢራ ድገመን” ብሎ ለኔም አዘዘልኝ። ለኃይለሥላሴ ክብር አጋጭተን ተጎነጨን። ዛሬ የተዋበ ምክር አፈር አባቷ መብላቷ ነው። አሁን ወደ አራተኛ ድራፍት ተሸጋገርኩ። አፌ ሲፍታታ እየተሰማኝ ነው፣ ስለ ኃይለሥላሴ ሰፋ ያለ መግለጫ ሰጠሁ። ስለ ፊደላችን አወራሁ። ላሊበላና አክሱምም አልቀረኝ። ይሄንን የሚያውቁም የማያውቁም የጨዋታችን ተካፋይ ሆነው ቆዩ።

አሁን ቤቷ ሞቅ ብላለች፣ ሁሉም ሰው እያወራ ነው። አንዲት ሴት መጥታ ጎኔ ካለው ጠባብ ስፍራ ተውተፈች። ከሷና ከሰውዬው ማኻል በመሆኔ ትንሽ የመጨነቅ ስሜት ተሰማኝ። ሆኖም ደስታዬን አልነጠቀኝም። ሞቅታዬ ግን እየጨመረ ሄዷል። ምናልባት መጠጤን ንረት የሰጠው ሰውዬው ከድራፍቱ ጋር የጋበዘኝ ባለአጭሯ መለኪያ አልኮል ሳትሆን አትቀርም። ግን ጣፍጣኛለች። አቤት ከዛ በኋላ ድራፍቱ ደግሞ ሲጥም፣ ላላዬው ወስኜ የተውኩትን የግርግዳ ሰዓት ተመለከትኩት ከሌሊቱ አስራ ሁለት ሰዓት ተኩል። የራሱ ጉዳይ! …

ሰውዬው እንደገና ጨዋታውን ከኔ ጋር አደረገ፤ ”ጌታው የት ሆቴል ነው የምትሠራው?” አለኝ ብዙ ማምሸቴ ሳይገርመው አልቀረም።

“የትኛውም ሆቴል አልሠራም”

”አሃ! ሌላ ሥራ ነው ያለህ ማለት ነው?”

“የለም! ጨርሶ ሥራ የለኝም።” ትንሽ ቆይቼ “ሥራ እየፈለኩ ነው።” የሚል አከልኩ። ሰውዬው ሲያስብ ከቆዬ በኋላ፣ ወደ ባለቤቱ እያመላከተኝ “እሱ አንዳንድ ጊዜ የሚረዳው ሰው ይቀጥራል። ምናልባት የሚፈልግ ከሆነ ብጠይቀው ምን ይመስልኻል” አለኝ።

“ጥሩ ሀሳብ ነው”።

ባለቤቱ ወደኛ ሲቀርብ “ይሄ ልጅ ሥራ ይፈልጋል። ምናልባት አንተጋ ይገኝ ይሆን” አለው።  

ትንሽ ሲያስብ ከቆየ በኋላ ”አንድ አዲስ ሥራ ሊኖረኝ ይችላል” አለ።

“ምን አይነት ሥራ?”

ስለሥራው በሃገራቸው ቋንቋ ተናገረ።

ጠያቂው ይስቅ ጀመር። ሁሉንም ትሰማ የነበረችው ጎኔ የተቀመጠች ሴት ፈጣን በሆነ ሁኔታ መልስ ሰጠች። ንግግሯ ቁጣ ያዘለ ነበር። ሁሉም በጉዳዩ ላይ ጣልቃ ገብቶ መናገር ጀመረ። የሚሉት ባይገባኝም መነሻው የኔ ሥራ ጉዳይ መሆኑ ገብቶኛል። ተጯጩኸው ተጯጩኸው ሲያበቁ አቆሙ። ይበልጥ ትቆጣ የነበረችው ሴትየዋ ነበረች።

ስለጉዳዩ ሰውዬውን ልጠይቅ ፈልኩ። “ምንድነው ያለህ ስለ ሥራው?”

”ፌዘኛ! ሰው ነው እባክህ፣ ለቁም ነገር የታደለ አይደለም አለኝ።”

“ለምን? ምን እንዳለህ አትነግረኝም?”

ወደኔ ጠጋ ብሎ ”እነዚያን የሟቾቹን ፎቶግራፎች ከተማውን በማዞር እያናፈስክ እንድትመልሳቸው ይፈልጋል። በቁማቸው መዝናናት የለመዱ በመሆናቸው ሰቅዬ ማስቀመጡ ግፍ ይሆንብኛል ነበር ያለው፣ ነገር ግን ቀልዱን ብዙዎቹ አልወደዱለትም” አለኝ። ንዴቴን ሳቄ አሸንፎት መሳቅ ጀመርኩ። እሱም ከቅድሙ ይልቅ አሁን ይበልጥ ይስቅ ጀመር። ከዚህ በኋላ ግን ብዙ መቆየት አላስፈለገኝም። መሄድ አለብኝ። እፊቴ ያለውን ድራፍ በአንድ ትንፍሽ ጨልጨ ሰውዬውን ተሰናብቼ ወደበሩ አመራሁ።

አቤት! ደስ ሲል፣ ሁሉ ነገር ደስ ደስ አለኝ። ያሉትን ሰዎች ሁሉ ወደድኳቸው። እየሳምኩ ልሰናበታቸው ሁሉ ፈለኩ። ፈገግታዬ ሞቋል። ይቺ ደስ የምትል አጋጣሚ ማለፍ የለባትም፣ አንድ ነገር ማድረግ አለብኝ። ምንም ነገር ለማድረግ ኃይሉም ችሎታውም ባሁኑ ሰዓት በጄ ነው። እናስ? ምን? መተላለፍያው ላይ ቆም ብዬ አሰብኩ። ምንም! በቃ! ምንም ሊመጣልኝ አልቻለም። ምንም ለማድረግ አለመቻሌን ሳስበው ወደ ብስጭት አመራሁ። እንደገና ደግሞ ዝፈን ዝፈን የሚል ስሜት ተሰማኝ፤ ምን ብዬ እዘፍናለሁ? የማይሆነውን፣ ወጥቼ የማደርገውን አደርጋለው ብዬ በቆሙት ሰዎች ማኻል እየተጋፋሁ ወደመውጫው ስቃረብ በርከት ያሉ ኢትዮጵያውያን ክብ ሰርተው ቢራ ሲጠጡ አየሁ።

“ሰላም ለናንተ ይሁን! ወንድሞቼ።” ቀኝ እጄን እንደሚባርክ አባት ወደ ላይ ዘረጋሁ።

“ሰላም ላንተም ይሁን!” ሞቅ ያለ አፀፋ ነበር የተሰጠኝ። ሞቅታ ደጉ ሁሉንም በየተራ እየጨበጥኹ፤ ስሜን አስተዋወቅኹ። የመጨረሻው ተጨባጭ እጄን ጠበቅ አድርጎ ይዞ፤ “እማውቅኽ አይመስለኝም፤ እዚህ ከተማ ነህ እንዴ?” አለኝ። አዲስ ነው ለማለት ተቸግሯል።

“አይደለሁም”

“ታዲያ ከየት መጣኽ?”

አናዳጅ ጥያቄ ነበር፤ ግን አልተናደድኹም። ወደ ጣሪያው አሳየኋቸው። ሁሉም ሽቅብ ተመለከቱ። “በዛ በኩል፣ ከሁለት ሰዓት በፊት በቀጥታ እዚህ ቤት ወረድኩ።” አልኳቸው፤ በጣም ሳቁ። ይቺ ንግግሬ ግን ”ፋሲል አየር ወለድ” የሚል ስም አትርፋልኝ እስከዛሬ መጠሪያዬ ሆናለች። ቢራ ጋብዘውኝ አብረን መጨዋወት ጀመርን። የኩምክና ወሬ እያወራሁላቸው፣ እየሳቅን፣ እየጠጣን፣ አመሸን። ከሆነ ሰዓት በኋላ ግን ያለውን አላወራውም። ላውራውም ብል አላውቀውም። በመጨረሻው ትዝ የሚለኝ ቢኖር አንድ ሰው ቤቴ በራፍ ድረስ እንደሸኘኝ ብቻ ነው።

* * *

ይህ የሦስት ወር የስደት ቆይታና የሁለት ቀናት ትዝታ ነው። እነሆ ይህ ከሆነ አስራ ስምንት ዓመታት አልፎታል። ዛሬ ነገሮች ሆኑ ተለውጠዋል። ተዋበ እዛው ቤት ከባለቤቱ ጋር ይኖራል። አሁንም አንደበተ ቁጥብና ጨዋ ነው። ልጆቹ ሥራ ይዘው ከቤት ወተዋል። አንዷ እዛው ከተማ ስትሆን፣ ሌላዋ ስፍራ ለውጣለች።

እኔ ከዛ ከተማ ወጣሁ። ኤልሳቤጥ ካሳዬ ቀጠረችኝ። ዛሬ ድርጅቱን በኃላፊነት ከሚያንቀሳቅሱት ሰዎች ማኻል አንዱ ነኝ። በሥራው ላይ ለአስራ አምስት ዓመታት ቆይቻለሁ። የኤልሳን እህት አግብቼ፣ አንድ ሴትና አንድ ወንድ ልጆች አሉኝ። ባለቤቴ ገነት ካሳዬ ትባላለች፣ ውብና ሸጋ አመል ያላት ልጅ ናት።

ተዋበ እንዳለኝ ጌዲዮንን አምጥቼዋለሁ። ምን ጌዲዮን ብቻ ትንሿ እህታችንም እዚኹ ናት። ጌዲ እንደኔ አልከፋውም፣ ወዲያው ሥራ ያዘ። ቆይቶ ታክሲ ነጂ ሆነ። ወፍሯል፣ በጣም ወፍሯል። ስማ ጌዲዮን እንዲህ ወፍረህ የሞትክ እንደሆን አንተን የሚሸከም የለም። እዛው የሞትክበት ነው በስብሰህ የምትቀር እንለዋለን፣ ጌዲ መልስ አለችው፤ ለዚህ አትስጉ ልክ ልሞት ትንሽ ሲቀረኝ አዳሬን ጉድጓዱጋ አደርጋለሁ። መቼም ገፋ አድርጋችሁ መክተት አያቅታችሁም። ይስቃል … አላገባም ብቻውን ቤት ይዞ ይኖራል።

ትንሿ እህታችን የኔ ቢጤ ቅብጥብጥ ሆነች። የውጪ ሀገር ኑሮን ልትለምደው አልቻለችም። እንደመጣች ያረፈችው ተዋበ ጋር ነበር። ሥራም አግኝታ ነበር። ከሁለት ወራት በላይ አልቆየችም ጥላ ወጣች።

”ለምን ተውሽው?”

”እኔ እንደዚህ ያለ ጥብስ ያለ ነገር አልፈልግም።” መልሷ እንዲሁ ነው ጥብስ ያለ ነገር። እኔጋ ቀየረች ከባለቤቴ ጋር አንድ ሰሞን ተወዳጁ። ጸጉር ይሠራሩ ነበር። አብረው ወጥተው አብረው ገቢ ነበሩ። ሥራም እኛ ድርጅት ያዘች። ዕድሜ ለኤልሳ እንኳን እህቴን አውቀዋለሁም ላልኩት አታሳፍረኝም፣ ”አላቃሽ ወንድሜ …” ትለኛለች። ለሣራ የሚስማማ ሥራ ነበር የሰጠቻት፤ ተወችው እንደገና ጌድዮን ቤት ሄደች። ከጌድዎን ቤት ወጥታ ተዋበ ጋር ተመልሳለች። አዲስ ሥራም ጀምራለች፤ ሁሉን ነገር ጥብስ ያለ ስለምትል ስሟን ትተን ”ጥብስ” ካልናት ቆይተናል።

በአበሻ በዓላት ተዋበ ቤት የመሰብሰብ ልምድ አለን። በአንድ የበዓል ሰሞን ከጌድዮን ጋር እዛች ቢራ ቤት ሄድኩ። ቤቷ እንደነበረች ቆየችኝ። ወንበሮቹ እንኳን የድሮ ቦታቸውን አለቀቁም። ወደ ባንኮኒው አመራሁ። ከባኮኒው ጀርባ መጠጥ የሚቀዳው ሌላ ሰው ነው። ማንንም መጠየቅ አላስፈለገኝም ከሙታን ፎቶዎች ማኻል ክፍቱን ቦታ ተመለከትኩ የድሮው ባለቤት ቦታውን ይዞ ገጭ ብሏል። ያንን ወዳጄንም ፈለኩ፣ እሱ እንኳን አይሞትም አልኩኝ በሃሳቤ፤ ግን ልክ አልነበርኩም። ከወዲኛው ጠርዝ በኩል ያቺን ቀይ መስመር ያለባትን ሸሚዝ እንደለበሰ ፎቶው ተሰቅሎ አየኹ። ሚስኪን! አሳሳቁ አሁን ድረስ አይረሳኝም። እዛ ከተማ በቆየሁበት ተጨማሪ ጊዜያት በተደጋጋሚ አገኘው ነበር።

ከጌዲዮን ጋር ቢራችንን በመጠጣት ላይ ነን። የዛን ጊዜውን ውሎና ታሪክ እስከዚህ ቤት ድረስ የተፈጸመውን ነግሬው ሳበቃ ልንሄድ ተነሳን። አሁን ግን እንደ ያኔው ዝፈን ዝፈን የሚል ስሜት ሳይሆን፤ አልቅስ አልቅስ እያለኝ ነው፤ ግን አላለቀስኩም። የዘፈንና የለቅሶ ጊዜያቱ መቀያየር እየገረመኝ እመውጫው በር ላይ እንደደረስን ”ፋሲል አየር ወለድ” የሚል የጅምላ ድምጽ ቤቱን ነቀነቀው፤ ስብዐት ለአብ!!! እነዛ ኢትዮጵያውያን ዛሬም እዛው ነበሩ።

የኢሳት ጋዜጠኛ ሲሳይ አጌና እህት የግፍ ሰለባዋ

0
0

10645174_704513272957683_171991983121885364_nዛ አስቂኝና ጥርስ የማታስከድን ወጣት ናት። ከእሷ ጋር ለደቂቃ አይደለም ለሰዓታት አብረህ ብታሳልፍ አይሰለችህም፤ በሳቅ ታንከተክትሃለች። አነጋገሯ ፈጠን..ፈጠን ያለ ነው። ..የሷ ቀልዶች አይረሱኝም።..በ1998 ዓ.ም የደረሰባት ነገር እጅግ አሳዛኝ ነው። የተቃዋሚ አመራሮች፣ ጋዜጠኞች፣ የቅንጅት ደጋፊዎችና ሰላማዊ ዜጎች በጅምላ እስር ቤት ሲጋዙ አጋጣሚ ጋዜጠኛ ሲሳይ አጌና ለሁለት ወር ገደማ እጁን ሳይሰጥ ተሰውሮ ነበር። የገዢው ባለስልጣናት (በረከትና መለስ ናቸው) ያሰማሯቸው ደህንነቶች ሲሳይን ፍለጋ ብዙ ሲማስኑ ነበር። ያላሰሱትና ያልተከታተሉት ሰው የለም፤ በመጨረሻ ግን እህቱን አፈኑ። እየደበደቡ ወደ ወለጋ ወሰዷት። ሴት ልጅ ልትቋቋመው ከምትችለው በላይ በዱላ አሰቃይዋት። « ሲሳይ የት ነው ያለው? ተናገሪ?» ሲሉ ፍዳዋን አስቆጠሯት። ምንም እንደማትውቅ ነገረቻቸው። ምንም ሲያጡ ወለጋ ላይ ፀጉሯን ላጭተው፣ በድብደባ ጐድተውና አቁስለው፣ እጅግ አዳክመው ጫካ ውስጥ አውሬ እንዲበላት ጥለዋት ሄዱ። ራሷን የሳተችው አቦነሽ (ቴሌ) ፈጣሪ ነፍስሽ ይትረፍ ሲላት ገበሬዎች አገኟት። ተሸክመው ወሰዷት። በመኖሪያ ጐጆዋቸው እንድታገግም አደረጉ። ከዚያም ስልክ ወደ አዲስ አበባ አስደወሉላት። ጋዜጠኞች ስፍራው ድረስ ሄደው አመጧት። ..እነሆ ከ8 ዓመት በኋላ ሌላ ክስ ከሙያ ባልደረቦችዋ ጋር ተመሰረተባትና በዚህ ሰሞን አገር ጥላ ተሰደደች። ይህ ግፍ መቆሚያው የት ይሆን!?…ስለተሰደዱት ጋዜጠኞች እመለስበታለሁ።

(በፎቶው የሲሳይ አጌና እህት በመሆኗ ብቻ በ1998ዓ.ም የተፈጸመባት ግፍ ይህን ይመስላል)

Source- freedom4ethiopian.

የተማሪዎች ተቃውሞ ተጠናክሮ ቀጥሏል

0
0
ነገረ ኢትዮጵያ 

• የኢትዮጵያ የባህር በር ለኤርትራ መሰጠቱ ስህተት ነው

• የኢኮኖሚ እደገቱ እውነት አይደለም 

• የትምህርት ስርዓቱ ወድቋል

• የተማረ ሰው ክብር አይሰጠውም

addis_universityአዲስ አበባ ውስጥ ሳውዝ ካምፓስ (ልደታ)፣ አቃቂ (AASTU)፣ ፍቼ የግብርና ኮሌጅ፣ ስድስት ኪሎ፣ አምስት ኪሎ፣ አራት ኪሎ፣ አአዲስ አበባ የቢዝነስና ኢኮኖሚክስት ትምህርት ክፍልና ሌሎችም አካባቢዎች ከነሃሴ 15 ጀምሮ ልጠና ላይ የሚገኙ የመጀመሪያ ዙር ሰልጣኞች ተቃውሟቸውን መሳማታቸውን እንደቀጠሉ የነገረ ኢትዮጵያ ምንጮች ገለጹ፡፡ ተማሪዎቹ ገዥው ፓርቲ አለ በሚለው እድገት፣ የባህር በር፣ የተማረው የማህበረሰብ በሚደርስበት በደል፣ የትምህርት ጥራት፣ የመምህራን የእውቀት ደረጃ ማነስ፣ ድህነትና አጠቃላይ ኢኮኖሚ ውድቀት ላይ ጠንከር ያለ አስተያየትና ተቃውሞ መሰንዘራቸውን ተገልጾአል፡፡

የኢኮኖሚ እድገት

ተቃውሞ ከገጠማቸው ጉዳዮች መካከል የኢኮኖሚ እድገት አለ የለም የሚለው ሲሆን ተማሪዎቹ ‹‹በአክሱም ዘመን ገናና የነበረችው ኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት በኢኮኖሚው መስክ ጭራ›› መሆኗን በመግለጽ እድገቱ አለ መባሉ ስህተት መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ተማሪዎቹ ጨምረውም ‹‹በቀን አንድ ጊዜ እንኳን መመገብ የማይችል ማህበረሰብ ይዘን አድገናል ማለት አንችልም፡፡›› በሚል እድገት አለመኖሩን ተከራክረዋል፡፡ ‹‹ሀገራችን ውስጥ የምግብ፣ የቤት፣ የትምህርት፣ የኔትወርክና ሌሎች ችግሮች አሉ፡፡ ስኳርና ዘይት ለመግዛት ህዝብ ቀበሌ ተሰልፎ ነው የሚውለው፡፡ በ400 ብር ደምወዝ ቤተሰብ የሚያስተዳድር ህዝብ ያለባት ሀገር የሌሎችን እድገት ፈዛ እያየች ያለችን ሀገር አድጋለች ልንል አይገባም፡፡›› ማለታቸው ተገልጾአል፡፡

በተመሳሳይም ‹‹2 በመቶ የሚሆነው የአሜሪካ አርሶ አደር ዓለምን በሚመግብበት በአሁኑ ወቅት 85 በመቶ አርሶ አደር ይዘን ለምን እንራባለን?›› የሚል ጥያቄ ማንሳታቸውንም የነገረ ኢትዮጵያ ምንጮች ጠቅሰዋል፡፡ ተማሪዎቹ ‹‹አድገናል ብለን ራሳችን ማወዳደር ያለብን ከ40 አመት ከነበረ ስርዓት ጋር መሆን የለበትም፡፡ እድገታችን መለካት ካለበት ከሌሎች አገራት ጋር ነው፡፡ መካከለኛ ገቢ ካላቸው አገራት በ2020 እንመደባለን ከተባለ መንግስት መቀየር ይኖርበታል፡፡ ምክንያቱም ይህን ስርዓት ለ20 አመት አይተነዋል፡፡ ባለፉት አመታት ለውጥ ሊያመጣ አልቻለምና በ2020ም ለውጥ ያመጣል ብለን አንጠብቅም፡፡›› የሚል ጠንካር ያለ ሀሳብም አቅርበዋል፡፡

እድገት ላይ ነው የሚባለው የኮንስትራክሽን ዘርፍ የጥራት ደረጃው ዝቅተኛ መሆኑን በተለይ በዘርፉ ትምህርታቸውን እየተከታተሉ የሚገኙ ተማሪዎች አንስተዋል፡፡ ተማሪዎቹ ‹‹እድገት የምንለው የህንጻዎችን ወደላይ ማደግ ወይንም መብዛት ሳይሆን የማህበረሰቡን አስተሳሰብና አኗኗር ዘይቤ መቀየር ነው፡፡›› ሲሉ ተከራክረዋል፡፡ በስልጠናው ወቅት ገዥው ፓርቲ የቻይናን ፈለግ ተከትሎ እድገት ማስመዝገቡን በመቃወም ‹‹ቻይና ከ2.3 እስከ 2.7 በመቶ እያደገች እንደሆነ ይነገራል፡፡ የእሷን ፈለግ ተከተለች የተባለችው ኢትዮጵያ ከ11.2 በመቶ በላይ አደገች ነው የሚባለው ከየት አምጥተነው ነው? ወይስ እንደ ቀን አቆጣጠራችን እድገታችንም ይለያያል?›› ሲሉም አሰልጣኖቹን ጠይቀዋል፡፡

የባህር በር
ተማሪዎቹ ለኤርትራ መሰጠቱ አግባብ እዳልሆነ፣ የባህር በርና ወደቡ ለኢትዮጵያ ቀጣይ እድገት፣ ደህንነትና ታሪክ አንጻር አስፈላጊ መሆኑን በመግለጽ ገዥው ፓርቲ በባህር በር ላይ ያለውን አቋምና ፈጸመ ያሉትን ስህተት ተችተዋል፡፡ ወደብ አልባ በመሆናችን ኢኮኖሚያችን ወደኋላ መቅረቱንም አንስተዋል፡፡ በሌላ በኩል ‹‹በአገራችን የሚመረቱ ሰብሎችና ፍራፍሬዎች ለአገር ውስጥ ገበያ የሚቀርቡት ከውጭ ከተላከው ሲተርፍ ነው፡፡›› በማለት በኤክስፖርት ዘርፍ ያለውን ችግር፣ አገር ውስጥ እየተፈጠረ ያለውን የኑሮ ውድነት ከዚሁ ችግር መመንጨቱን ጠቅሰዋል፡፡

የትምህርት ጥራት

ተማሪዎቹ የራሳቸውን ተሞክሮ በመጥቀስ የትምህርት ስርዓቱ ችግር ያለበት መሆኑን በመከራከሪያነት አቅርበዋል፡፡ ‹‹ለተማረ ሰው ክብር እየተሰጠ አይደለም፡፡›› በሚል የእነሱም እጣ ፈንታ ተመሳሳይ መሆኑን ስጋታቸውን ገልጸዋል፡፡ በተጨማሪም ‹‹የሚያስተምሩን አስተማሪዎች የእውቀት ደረጃ ጥያቄ ምልክት ውስጥ ነው፡፡ በየ ዩኒቨርሲቲው በአመራር ላይ የሚገኙ ግለሰቦች እውቀት የላቸውም፡፡›› በማለት ዩኒቨርሲቲዎች ላይ የተደቀነውን አደጋ አንስተዋል፡፡

ዲግሪ ይዘው በስራ ፈጠራ ስም በጥቃቅንና አነስተኛ እንዲደራጁ የሚደረገውን የተቃወሙት ተማሪዎቹ ‹‹የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ተደራጅተው ካፌ ከፈቱ፣ ኮብልስቶን አነጠፉ ሲባል ነው የምንሰማው፡፡ ለዚህ ስራ ደግሞ ዩኒቨርሲቲ መማር አያስፈልገውም፡፡ ይህን ስራ ለመስራት የሶስት ወር ስልጠና በቂ ሆኖ እያለ ዩኒቨርሲቲ መማር ባላስፈለ›› ሲሉ የትምህርት ስርዓቱ ውድቀት እንደገጠመው መግለጻቸውን ለማወቅ ተችሏል፡፡

ነገረ ኢትዮጵያ በቀጣይም የተማሪዎችን ጉዳይ እየተከታተለች ታቀርባለች!

Viewing all 15006 articles
Browse latest View live