Quantcast
Channel: Ethiopian News | ዘ-ሐበሻ | Latest News Provider | News For All
Viewing all 15006 articles
Browse latest View live

የወያኔው ኢንሳ በአዲስ መልክ የፌስቡክ ስም አጥፊ ፔጆችን/ገጾችን ሊያደራጅ ነው

$
0
0

=================ነቢል አህመድ ዘገፈርሳ=====================

facebook
ወያኔ የኢትዮጵያን ሕዝብ አንድነት እና ነጻነት ለመሸራረፍ ብሎም ለመበታተን ከሚጠቀምባቸው ዘዴዎች አንዱ በማህበራዊ ድህረገጹ ያሰማራቸውን ከተቃዋሚ ሃይላት ጋር ተመሳስለው የተቃዋሚ የፖለቲካ ድርጅት መስለው የተቃዋሚ ሃይሎችን ሎግ በመጠቀም እንዲሁም ለሽፋንነት በየመሃሉ የተቃዋሚ ድርጅቶችን መግለጫ እንደወሽመጥ በማስገባት በማታለል እና በማጭበርበር ላይ ተመስርተው ሲሰሩ የነበሩ ስም አጥፊ ገጾችን/ ፔጆችን በአዲስ መልክ ለማደራጀት በዚህ ሳምንት እረፍት እንዲወስዱ ያደረጋቸው መሆኑ ታውቋል።

ስም በማጥፋት ለውጥ ፈላጊ ሃይሎች በተለያዩ አክቲቪስቶች ላይ መጠራጠር እንዲያሳድሩ እና ጠቃሚ የተባሉ ጦማርያንን እንዲያጡ እና ትግሉ አቅጣጫውን እንዲስት በስፋት አዲስ የአሰራር ዘይቤ ለመቀየስ የተሳዳቢዎች የተዛልፊዎች እና የስም አጥፊዎች የማህበራዊ አካውንት እና ፔጆች እረፍት ላይ መሆናቸውን እና በተጠናከረ መልኩ ወደ ስራ እንደሚመለሱ በቅርብ የሚያውቋቸው ወዳጆቻቸው ተናግረዋል።

በዚሁም መሰረት በዜጎች መካከል ከባድ ጥርጣሬን ያጭራሉ የተባሉ የፈጠራ ጽሁፎች እና የሞቱ ሰዎች ፎቶዎችን በመጠቀም የተለያዩ የፌክ ወንጀሎችን በመጻፍ እንድሁም ከብልግና እና የሰውን ክብር ከሚያዋርዱ አዳዲስ ብካይ የሃሰት መረጃዎች ጋር ወዘተ ተያይዘው ወደ ማህበራዊ ድህረገጾች እርፍታቸውን ጨርሰው እንደሚመጡ ታውቋል።


Hiber Radio: ግብጽ በሳተላይት የአባይ ግድብን ሰልላ የውሃ ማቆሪያው ግንባታ አለመጀመሩን ደርሼበታለሁ አለች፤ (የኢ/ር ግዛቸውና የዳንኤልን ቃለምልልስ ይዘናል)

$
0
0

ጋዜጠኛ ሃብታሙ አሰፋ

ጋዜጠኛ ሃብታሙ አሰፋ


የህብር ሬዲዮ ነሐሴ 11 ቀን 2006 ፕሮግራም

>

ኢ/ር ግዛቸው ሽፈራው የአንድነት ፕሪዝዳንት ስለ ውቅታዊው የአንድነት አቋም ተጠይቀው ከሰጡት ምላሽ (ሙሉውን ያዳምጡት)

>

አቶ ዳንኤል ተፈራ የአንድነት የድርጅት ጉዳይ ሀላፊ አንድነት ፓርቲ የውህዱን ኮሚቴ ስራውን እንዲቋረጥ ማድረጉን በመቃወም ከካቢኔ አባልነታቸው ቢለቁም ትግሉን አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ገልጸዋል(ሙሉውን ያዳምጡት)

በአሜሪካ ሚዙሪ ግዛት ፈርጉሰነን ላይ በፖሊስ የተገደለው ጥቁር አሜሪካዊ ወጣትና ለሕዝቡ ተቃውሞ በፖሊስ የተሰጠው ምላሽ ያመጣው ጣጣ (ልዩ ጥንቅር)

<...> ጋዜጠኛ ኤልያስ ገብሩ ስለ ወቅታዊው ጉዳይ ለህብር ከሰጠው ቃለ ምልልስ የተወሰደ(ሙሉውን ያዳምጡት)

ዜናዎቻችን

የዓለም የጠየና ድርጅት ኢቦላ ኢትዮጵያን ያሰጋታል ሲል አስጠነቀቀ

የመኢአድና የአንድነት ውህደት ሊቀለበስ አይችልም ተባለ

አንድነት ፓርቲ ጠንካራ በመሆኑ በውስጡ የተፈጠሩ ችግሮችን በራሱ ተቋም እንደሚፈታ ተገለጸ

ኢ/ር ግዛቸው የውህዱን ኮሚቴ ያፈረስነው ውህደቱን ለማጠናከር ነው አሉ

ግብጽ በሳተላይት የአባይ ግድብን ሰልላ የውሃ ማቆሪያው ግንባታ አለመጀመሩን ደርሼበታለሁ አለች

ጅቡቲ በቅርቡ በኤርትራ የታገቱባት ወታደራዊ መኮንን በአስቸኳይ እንዲለቀቁ ጠየቀች

የኢህአፓ አባላትና መሪዎች በአንድነት ተጠናክረው ክፍፍልን በማስወገድ ለትግል እንዲነሱ ትንሳዔ ኢህአፓ ጥሪ አቀረበ

ሌሎችም ዜናዎች አሉ፦

መልካ የልደት በዓል አመዬ ምኒልክ

$
0
0

ዳግማዊ ዓፄ ምኒልክ ከአባታቸው ከሸዋው ንጉስ ኃይለ መለኮት ሣህለ ሥላሤና ከእናታቸው ወይዘሮ እጅጋየሁ ለማ አድያም ቅዳሜ ነሐሴ 12ቀን 1836ዓ.ም ደብረ ብርሃን አካባቢ አንጎለላ ከሚባል ሥፍራ ተወልደዉ በአንጎለላ መቅደላ ኪዳነ ምሕረት ቤተ ክርስቲያን ክርስትና ተነሱ::
አያታቸዉ ንጉስ ሣህለ ሥላሴ የልጁን መወለድ ሲሰሙ “ምን ይልህ ሸዋ” በሉት ብለዉ ስም አወጡ::
እሳቸዉ “…… ምኒልክ በሚል ስም የሚነግስ ንጉሥ ኢትዮጵያን ታላቅ ያደርጋታል” የሚል ትንቢት ስለ ነበር ‘ምኒልክ’ የኔ ስም ነው ብለዉ ነበር::
ሆኖም በህልማቸዉ ከልጁ አብረው ቆመዉ ከሳቸዉ ጥላ የልጁ ጥላ በልጦ በእግር የረገጡትን መሬት ሲያለካኩ እሳቸዉ ከረገጡት ልጁ የረገጠዉ ረዝሞ አዩ::
ከዚህ በኃላ “ምኒልክ የኔ ስም አይደለም የሱ ነው ስሙን ምኒልክ በሉት” ብለዉ አዘዙ::

ጳዉሎስ ኞኞ
ከአጤ ምኒልክ መፅሐፍ

Emmye-Menelik-640x330

Happy Birthday Emperor Emye Menelik II

Emperor Emye Menelik II of Ethiopia was born on August 17, 1844 near Angolela, Debire Birhan, Ethiopia. He died on 12 December 1913). He was the King of Shewa (1866–89), then the Emperor of Ethiopia from 1889 to the first decade of 1910.

Happy Happy Birthday King!

We owe him boundless respect and honor and are indebted of his un-payable sacrifices.

debirhan

ወጣት ጥላዬ ታረቀኝ ዛሬ ፍድር ቀርቦ የዋስትና መብቱ ሳይጠበቅ ለዓርብ ቢቀጠርም የትግርኛ ሙዚቃ ለምን ተከፈተ ብሎ በሰው ላይ ጉዳት አድርሷል በሚል 2ኛ የክስ መዝገብ ተከፍቶበታል፡፡

$
0
0

ፍኖተ ነፃነት

10606390_684528351632102_6265250781347686507_nበ4/12/06 እሁድ ማታ በደህንነት ኃይሎች በቁጥጥር ስር የዋለውና በእስር ላይ የሚገኘው ወጣት ጥላዬ ታረቀኝ በዛሬው እለት ፍርድ ቤት ቢቀርብም ፖሊስ ከሳሹን ስላላገኘሁትና የህክምና ማስረጃውን ስላልደረሰልኝ የጊዜ ቀጠሮ ይፈቀድልኝ ያለ ቢሆንም ወጣት ጥላዬ መርማሪው የምርመራ ስራን እየሰራ አይደለም ይልቁንም ራሱ ቢሮ የያዙኝ ደህንነቶች እየመጡ መርማሪው ባለበት ከእኛ ጋር ለመስራት ፈቃደኛ እስካልሆንክና የምንሰጥህን ተልዕኮ እስካልፈፀምክ እዚህ ትበሰብሳለህ እንጂ አትወጣም እያሉ እንደሚዝቱበት ለፍርድ ቤቱ ቢያስረዳም ፍ/ቤቱ ፖሊስ ለ16/12/2006 ፖሊስ መረጃዎቹን አጠናቆ እንዲያቀርብ እስከዛ የዋስና መብቱ ተቀባይነት አለማግኘቱን ብይን ሰጥቷል፡፡

ወደ እስር ቤት ሊሄድ በሚዘጋጅበት በድጋሚ ተጠርቶ 2ኛ የክስ መዝገብ እንደተከፈበት እና ክሱም በ12/10/2006 ዓ.ም ከምሽቱ 4፡30 ላይ የትግርኛ ሙዚቃ እንዴት ይከፈታል በማለት በሰላም የሚዝናኑ ግለሰቦች ላይ ጉዳት አድርሶ ተሰውሯል የሚል ሲሆን ስለቀቀረበበት ክስ የተጠየቀው ጥላዬ እኔ ከአካባቢዬ አልተሰወርኩም ሲይዙኝም ከቤቴ በር ላይ ነው እስከዚህ ሰዓትም አላመሽም ፖሊስ እያቀረበ ያለው ክስ ከሳሽ በሌለበት ራሱ እየፈጠረ መሆኑን ፍርድ ቤቱ እንዲረዳልኝ እና የአንድነት ፓርቲ አባል በመሆኔ ባለኝ የፖለቲካ አመለካከት ጫና ለማሳደር የተወጠነ ውጥን መሆኑን መርማሪው ራሳቸው ያውቃሉ በማለት አስረድቷል ፡፡ፖሊስ ለምን ጉዳት የደረሰበትን ግለሰብ እንዳላቀረበና 2ወር ሙሉ ፖሊስ የት ነበራችሁ ብሎ ፍ/ቤቱ ቢጠየቅም ከሳሽ ለጊዜው እዚህ ስለሌለና ልናገኘው ባለመቻላችን የህክምና ማስረጃውን እንድናቀርብ ይፈቀድልን በማለቱ ፍርድ ቤቱ የፖሊስን ማስረጃ ለመመልከት በ2ኛው ክስ ለ14/12/2006 ዓ.ም ለ3፡00 ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡ ፖለስ እስካሁን በጥላዬ ላይ ክስ የመሰረተውን ከሳሽን ሊያቀርብ ካለመቻሉም ባሻገር ፍ/ቤቱን የህክምና ማስረጃ እንዳቀርብ ይፈቀድልኝ ማለቱ አግራሞትን ጭሯል፡፡

ደብረ ታቦር ወይንም ቡሄ! በመላው ሀገራችን በየዓመቱ ነሐሴ ፲፫ ቀን የሚከበር በዓል

$
0
0

ደብረ ታቦር ወይንም ቡሄ! በመላው ሀገራችን በየዓመቱ ነሐሴ ፲፫ ቀን የሚከበር በዓል ሲሆን፤ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ከምታከብራቸው ዓቢይ (ዋና) በዓላት አንዱ ይሄ ‘ደብረ ታቦር’ የምትለው የቡሄ በዓል ነው።

buhe

የዚህ በዓል መሠረት የክርስቲያን እምነት ሲሆን፣ ደብረ ታቦር በግዕዝ የታቦር ተራራ ማለት ነው፡፡ የታቦር ተራራ የሚገኘው አሁን ፍልስጥኤም ተብሎ በሚጠራው ሀገር ነው፡፡ ደብረ ታቦር ወይንም የታቦር ተራራ ኢየሱስ ክርስቶስ ሦስት ደቀመዛሙርቱን ይዞ ወደ ተራራው የወጣበትና ፊቱ እንደፀሐይ የበራበት ልብሱም እንደብርሃን ነጭ የሆነበት ቦታ ነው፡፡ ይህ ቦታ ጌታ ብርሃነ መለኮቱን የገለጠበት ተራራ ነው።

የማቴዎስ ወንገል ምዕራፍ ፲፯፦ ቁጥር ፩ እስከ ፭ ” ከስድስት ቀንም በኋላ ኢየሱስ ጴጥሮስንና ያዕቆብን ወንድሙንም ዮሐንስን ይዞ ወደ ረጅም ተራራ ብቻቸውን አወጣቸው። በፊታቸውም ተለወጠ፥ ፊቱም እንደ ፀሐይ በራ፥ ልብሱም እንደ ብርሃን ነጭ ሆነ። እነሆም፥ ሙሴና ኤልያስ ከእርሱ ጋር ሲነጋገሩ ታዩአቸው። ጴጥሮስም መልሶ ኢየሱስን ጌታ ሆይ፥ በዚህ መሆን ለእኛ መልካም ነው፤ ብትወድስ፥ በዚህ ሦስት ዳስ አንዱን ለአንተ አንዱንም ለሙሴ አንዱንም ለኤልያስ እንሥራ አለ። እርሱም ገና ሲናገር፥ እነሆ፥ ብሩህ ደመና ጋረዳቸው፥ እነሆም፥ ከደመናው። በእርሱ ደስ የሚለኝ የምወደው ልጄ ይህ ነው፤ እርሱን ስሙት የሚል ድምፅ መጣ።”

ዓቢይ መሠረቱ ይሄ ሲሆን፣ በአገራችን የክረምቱ አፈና ተወግዶ የብርሃን ወገግታ የሚታየውም በዚህ በዓል አካባቢ ስለሆነ ይቺ ዕለት ‘ቡሄ’ የሚለውን ስያሜ አገኘች። ቡሄ ማለት ገላጣ፣ የተገለጠ ማለት ነው፡፡

በገጠርም ሆነ በየከተማው ልጆች ጅራፋቸውን ገምደው ሲያጮሁ (ሲያኖጉ) ይሰነብታሉ። እናቶችም ለበዓሉ ዝግጅት ስንዴ ሲለቅሙ፣ ሲፈትጉ፣ ሲፈጩ ይሰነብታሉ። ጌታችን ብርሃነ መለኮቱን በገለጠበት ዕለት ጊዜው ምሽት ነበር፡፡ እረኞችም ከብርሃኑ የተነሣ እየተገረሙና እየተደነቁ ወደ ቤት አልተመለሱም ነበር፡፡ የልጆቹን መዘግየት ያዩ ወላጆች ችቦ አብርተውና ዳቦ ይዘው ፍለጋ ወጡ፡፡ ታዲያ ያንን ማስታወሻ «ቡሄ» ለሚሉ ልጆች ሙልሙል ዳቦ የሚሰጠውና ችቦ በማብራት በዓሉን የምናከብረውም ከዚህ በመነሣት ነው፡፡

ቡሄ በሉ፣ ልጆች ሁሉ
ቡሄ መጣ፤ ያ መላጣ
ቅቤ ቀቡት፣ እንዳይነጣ

ክፈትልን በሩን
የጌታዬን

እዚያ ማዶ ነጭ ሻሽ
እዚህ ማዶ ጥቁር ሻሽ
የእኔማ ጌታ ነጭ ለባሽ።

የወንዜው ነብር የወንዜው ነብር
የኛማ ጌታ ሊሰጡን ነበር።

ሆይ ሾህዬ ሎሚታ
ልምጣ ወይ ወደማታ።

ለብሩ ነወይ ነወይ ሽጉዱ
በአባትህ ጊዜ ሰንጋ ነው ልምዱ

 

 

ሻእቢያ ከከረን እና ከአስመራ ጦሩን ወደ ተሰንይ ማስፈሩን ተከትሎ ወያኔ ተጨማሪ ጦር ሲያጓጉዝ ዋለ።

$
0
0

Minilik Salsawi (ምንሊክ ሳልሳዊ)

የመከላከያ ሰራዊቱ ሊከዳ ይችላል በሚል ስጋት የወያኔ ጄኔራሎች ሲመክሩ ውለዋል።

ከሩሲያ ጋር የጦር ልምምድ ስምምነት እንዳደረገ የሚነገርለት የኤርትራ ገዥ ቡድን ሻእቢያ ከባለፉት ወራቶች ጀምሮ ጦሩን ወደ ደቡባዊ የኤርትራ ግዛቶቹ በመሰብሰብ ላይ መሆኑን ተከትሎ ወያኔም እንዲሁ ባለፈው ካሰፈረው ሰራዊት በተጨማሪ ከትላንትና ጀምሮ ከባድ የጦር ተሽከርካሪዎችን እና ተጨማሪ የጦር ሰራዊት በአከባቢው በማስፈር ላይ መሆኑ ታውቋል።

Ethio-army2 (1)አሜሪካ እና ሩሲያ በአከባቢው ያላቸውን የበላይነት ለመቀዳጀት ፉክክር በገቡበት በዚህ ወቅት አከባቢው የጦርነት ቀጠና እንደሚሆን ቀድማ አሜሪካ በበረራ ደህንንነ ሰበብ ሹክ ባለችበት ሰአት እንዲሁም የሻእቢያ ተቃዋሚ ሃይሎችን ወያኔ በገንዘብ እና በቅስቁስ እየረዳ ባለበት ጊዜ በተጨማሪም በአግል ወያኔያዊ ትእቢት እየዛተ እንዳለ ሲሆን ለወያኔ ከፍተኛ ስጋት የሆኑበት ኢርታራ ውስት የመሸጉ ተቃዋሚ ሃይላት ስለሆኑበት በጭቆና የተምረረው ምከልከያ ሰራዊት ተቃዋሚዎችን ይቀላቅላል የሚል ከባድ ስጋት በሕወሓት ጄኔራሎች ላይ መከሰቱን ምንጮች ጠቁመውል።

ወያኔ በቅርቡ ከዩክሬይን ያስገባችቸን ቲ-72 ዘመናዊ ታንኮች በጦርነት ላይ ለማሰለፍ ወደ ሰሜን እያጓጓዘ ሲሆን ሻእቢያ በበኩሉ ሩሲያ ሰራሽ የሆኑ ዘመናዊ ታንኮች ሚሳኤሎች እና ከባባድ መሳሪያዎች፡ጸረ አይሮፕላን መድፎችን በአከባቢው አስፍሯል። ወያኔ ዘመናዊ መሳሪያ እና በታንክ ላይ የተጠመዱ መድፎችን ቢያምጣም በመክላከያ ሰራዊቱ ላይ ምንም አይነት መተማመን እንዳሌለው እየተናገረ ሲሆን በሰሜናዊ ትግራይ ብግብርና ሙያ ላይ ከነሙሉ ትጥቃቸው ያሰፈራቸውን የቀድሞ ታጋዮች እየቀሰቀሰ መሆኑ ሲታወቅ ህዝቡ ጦርነት እንደተሰላቸ እና ባለው ስርአት ላይ እምነት እንዳጣ በግልጽ እየተናገረ መሆኑ ታውቋል።

በሰራዊቱ ያልተማመነው ወያኔ አንድ የወሰደው እርምጃ ከሱዳን ጋር ያደረገውን የሰራዊት ቅልቅል ሲሆን ይህም ተቀላቅሎ መስራት በሰራዊቱ መኮንኖች ዘንድ ተቀባይነት አለማግኘቱ ታውቋል። የምዕራብ ኢትዮጵያን መሬት ለሱዳን ለመስጠት ያሰበውን አገር የማጥፋት ሴራ ተግባራዊ ለማድረግ መሆኑን እና ሰራዊቱም ይህንን ተረድቶ ላገሩ ክብርና ታሪክ እንዲቆም ህዝቡ እየትናግረ ሲሆን የተደረገው የሰራዊት ውህደት ሱዳን በዳርፍርና ምስራቅ ሱዳን እንዲሁም ከደቡብ ሱዳን አቅጣጫ ላለበት ጦርነት በስምምነታቸው መሰረት የኢትዮጵያ ወታደሮች እንዲዋጉለት ለማድረግና ወያኔም በዚህ ጉዳይ ላይ መስማማቱን እናም በመከላከያ ሰራዊት ያለ የኢትዮጵያ ወጣት በጎረቤት አገሮች የበረሃ ሲሳይ ከመሆን ራስን እንዲታደግ አስተያየት ሰጪዎች አሳስበዋል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ ከአዲስ አበባ የሚወጡ ዘገባዎች መጭውን የወያኔ የጦርነት ዝግጅት ተከትሎ የመከላከያ ሰራዊቱ በመክዳት ከተቃዋሚ ሃይሎች ጋር ሊቀላቀል ይሽላል በሚል ስጋት ስብሰባ ተቀምጠው መዋላችውን ምንጮች ጠቁመዋል። በኤርትራ የሚንቀሳቀሱ የተቃዋሚ ሃይሎች የሚያወጡት መግለጫ በሰራዊቱ ላይ የሚፈጸመው ዘረኝነት እንዲሁም ብዝበዛ እና ከሃገሪቱ ጥቅሞች አንጻር እየተደረገ ያለው ብሄራዊ ውርድት በእጅጉ አሳሳቢ ደረጅ ልይ መድረሱ ሕዝቡ ለስር አቱ ያለው ጥላቻ መበራከቱ እንዲሁም ከዚህ ቀደም በባድመ ጉዳይ የተፈጸሙ መንግስታዊ ማጭበርበሮች እና የመሳሰሉት ግኡዳዮች ሰራዊቱ ይከዳል የሚል ከባድ ስጋት ያላቸው መሆኑን ያወሱት ጄኔራሎቹ በመከላከያ ሰራዊቱ ላይ እምነት በማጣትቸው ትግራይ ያለው የሕወሓት ታጣቂ ሃይል ከጀርባ እንደ ደጀን እንደ መተማመኛ እንደሚወስዱት መክረዋል።

ሰራዊቱ ያለውን ስርአት በተመለከት ደስተኛ ስላልሆነ እንዲሁም ሕዝቡ የሚፈልገው ለውጥ እንጂ ጦርንት ስላልሆነ ወያኔ በመጭው ሊያደርገው ያሰበው ጦርነት ከባድ ኪሳራ ያስክትልበታል ተብሎ ተገምቷል።

የአያት ኮንዶሚኒየም ነዋሪዎች ሰልፍ እንደወጡ ተነገረ

$
0
0

ለ6 ቀናት መብራት የተቋረጠባቸው የአያት ኮንዶሚኒየም ነዋሪዎች ሰልፍ እንደወጡ ለነገረ ኢትዮጵያ ተናገሩ፡፡ የአካባቢው ነዋሪዎች ለ6 ብሎክ ያስፈልግ የነበረው ትራንስፎርመር ለ12 ብሎክ እንዲያገለግል በመደረጉ መብራት አጥተን ሰንብተናል ያሉት ነዋሪዎቹ ባቀረቡት አቤቱታ መሰረት በትናንትናው ዕለት መብራት ኃይል የትራንስፎርመሩ ችግር መሆኑን ተረድቻለሁ ብሎ ትራንስፎርመር ቢቀይርም ማታ ላይ የመብራት ኃይል ሰራተኛ ነን ያሉ ሰዎች ከሌሎች ሰዎች ጋር በመመሳጠር ፊውዞቹን ፈትተው ሊወስዱ ሲሊ እንደያዙዋቸው ገልጸዋል፡፡
ayat condos
ሁኔታውንም ‹‹ትናንትናም ሌላ ትራንስፎርመር አምጥተው ቀየሩ፡፡ ማታ ላይ ግን ተመልሰው መጀመሪያ የመጣውን ትራንስፎርመር ከሌሎች ሰዎች ጋር በመመሳጠር ፊውዞችን ለመቀየር ሲሞክሩ የብሎኩ ነዋሪዎች እጅ ከፍንጅ ይዘዋቸዋል፡፡›› ሲሉ አቶ ብርሃኑ የተባሉ የአካባቢው ነዋሪ ለዝግጅት ክፍላችን ደውለው ገልጸዋል፡፡

‹‹ጉዳዩን ወደ ፖሊስ በመውሰድ እስከ 5 ሰዓት ድረስ መፍትሄ እንዲሰጠን የጣርን ሲሆን የመብራት ኃይል ኃላፊ ነኝ ያሉ አቶ ኢሳያስ የሚባሉ ሰው ጠዋት መፍትሄ እንዲሚሰጠን ገልጸውልን ነበር፡፡›› ያሉት ስማቸው እንዳይጠቀስ የፈለጉ ሌላ የአካባቢው ነዋሪ መፍትሄ ባለማግኘታቸው ህዝብ መብራት ኃይል መፍትሄ እንዲሰጠው መውጣቱን ገልጸዋል፡፡ ይሁንና ህዝቡ ወጥቶ ወደ መብራት ኃይል ለመሄድ እየተሰባሰበ እያለ መፍትሄ እንሰጣችኋለን ብለው የመጡት ሰራተኞች ‹‹ሌላ የምንቀይረው እቃ አለ›› ብለው መመለሳቸውንና ሌሎች አመራሮች መጥተው ማታ ሰው ደብድባችኋል፣ የመብራት ኃይል ሰራተኞች ሳይሆኑ እቃዎቹን እናንተ ናችሁ የሰረቃችሁት በሚል ህዝቡ ወንጀል እንደፈጸመና ለፍትህ እንደሚያቀርቡት መዛታቸውን ነዋሪዎቹ ገልጸዋል፡፡

‹‹ማታ ህዝቡ ፊውዞቹን አስመለሰ እንጅ አልተደባደበም፡፡ ይህም ቢሆን የፖሊስ እንጅ የመብራት ኃይል ባለስልጣናት ስራ አይደለም፡፡ እንዴት ህዝብ ሌባ ይባላል›› ያሉት ነዋሪዎቹ በመብራት ኃይል ባለስልጣናት ማዘናቸውንና አሁንም መፍትሄ እንዲሰጣቸው ለመጠየቅ ወደ መመስያ ቤቱ በመሄድ ላይ መሆናቸውን ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡

በማይጨው ሰላማዊ ሰልፍ ለማድረግ ሕዝቡ ጥያቄ አቀረበ

$
0
0

ከአንዶም ገብረሥላሴ

በፌደራል መንግስት የተፈቀደ የማይጨው ተክኒክ ኮሌጅ ቀስበቀስ ወደ ዩኒቨርስቲነት የሚያደርገው እድገት በትግራይ ክልል አስተዳር ወደ ሌላ ቦታ በመዛወሩ የኣከባቢው ህዝብ ማስቆጣቱ መዘገቡ ይታወሳል። የማይጨውና አካባቢዋ ህዝብ በክልል ትግራይ አስተዳደር የኮሌጁ ወደ ዩኒቨርስቲ እድገት በመከልከላቸው ትናንት ከፍተኛ አድማ እንዲያካሂድ ምክንያት ሆነዋል። ባጃጆች፣ የመንግስት ሰራተኞች፣የዩኒቨርስቲ ተማሪዎች የኮሌጁ ማህበረሰብና የከተማው ኑዋሪ የስራ ማስቆም አድማ ኣድርገው ውለዋል። ለእሁድ 18 / 12 / 2006 ዓ/ ም የሰላማዊ ሰልፍም ለከተማው አስተዳዳሪዎች ጥያቄ አቅርበዋል።
የፌደራል መንግስት ደብዳቤ ተመልከቱ።
ነፃነታችን በእጃችን ነው…!
Maychew 1

Maychew 2


የሕዳሴ አብዮት ለፖለቲካው ( አስራት አብርሃም)

$
0
0

አስራት አብርሃም

asrat abereha

አስራት አብርሃም

ወዳጄ ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ የህዳሴው አብዮት አይቀሬ እርግጠኛ ሆኗል፤ እኔም ያለኝ ግምት ተመሳሳይ ነው። በመሆኑም የዛሬው ፅሁፌ የሚያተኩረው የህዳሴው አብዮት እንዴትና የት ይጀምር? በሚለው ርዕሰ ጉዳይ ላይ ይሆናል። በእኔ እምነት የህዳሴው አብዮት መጀመር ያለበት ከራሱ ከተቃውሞ ጎራ ነው የሚል ነው። ምክንያቱም የለውጡን ሀይል የሚመራው ይሄ የተቃውሞ ጎራ ስለሚሆን በመጀመርያ ውስጡን ማጥራትና ማጠናከር ስላለበት ነው። ስለዚህ፣ ከሁሉም ነገር በፊት የተቃውሞ ጎራው በትክክልና በተገቢው ሁኔታ እንዲታደስና እንዲለውጥ ማድረግ ያስፈልጋል ማለት ነው። ስለፖለቲካው መታደስና መለወጥ ሲታሰብ ደግሞ እንዴት ነው የሚታደሰው? እንዴት ነው የሚለወጠው? የሚሉትን ጥያቄዎች ማንሳት ተገቢ ይሆናል። የመጀመርያው ነገር፣ እስካሁን ከተጓዝንበት ኋላቀርና ውጤት አልባ የትግል ስልት የሚያወጣን፣ የተለየ ያካሄድ ለውጥና የሰላማዊ ትግል እንቅስቃሴ ለማደረግ የሚያስችለን ብቁ የሆነ ፖለቲካዊ አመራር ወደፊት እንዲመጣ ማድረግ ነው። በተለይ ደግሞ ፖለቲካዊ ትግሉ በአስራር፣ በአደረጃጀት፣ በዴሞክራሲያዊ ባህልና በበሳል አመራር ማጠናከርና ማነፅ ቀዳሚው ተግባር ነው የሚሆነው።


በቅርቡ ሊካሄድ ታስቦ የነበረውና በኋላ በምርጫ ቦርድ ምክንያት ለጊዜው የተቋረጠው የአንድነትና የመኢአድ ውህድ ፓርቲ ፕሬዝደንት የሚሆን ሰው ለመምረጥ በአንድነት ውስጥ የታየው እጅግ ማራኪና አስተማሪ የሆነ ዴሞክራሲያዊ ውድድር፣ የሰለጠነ የእጩዎቹ ደጋፊዎች ቅስቃሳ የዚሁ የህዳሴው አብዮት ጅማሮ አድርጌ ነው የምወስደው። ይሄ ዴሞክራሲዊ የሆነ ውድድር በማህበራዊ ሚዲያዎች፣ በጋዜጦችና በመፅሔቶች በጉልህ ይታይ ስለነበር የተቃውሞ ጎራ አባላት፤ ህዝቡ፣ የገዥው ፓርቲ ሰዎችም ጭምር በአንክሮ እንዲከታተሉት ምክንያት ሆኗል። ይህ እንቅስቃሴ አንድነትን ወደ ተሻለ ከፍታ የሚወስደው ከሆኑም ባሻገር ልክ እንደ ዐረቡ አብዮት ወደ ሁሉም የተቃውሞ ጎራ የሚዛመት አዲስ መንፈስ ነው ብዬ ነው የማስበው። ምንም እንኳ በተወሰነ መልኩ በዴሞክራሲያዊ ውድድርና በውስጣዊ መከፋፋል መካከል ያለውን ልዩነቱ በትክክል ያልገባቸው ወይም እንዲገባቸው ያልፈለጉ አንዳንድ ሰዎች የሚፈጥሩት ችግር የነበረ ቢሆንም በአጠቃላዩ እንቅስቃሴ ሲታይ ግን በኢትዮጵያ የፓርቲዎች ታሪክ ውስጥ በአዲስነቱ፣ በፈር ቀዳጅነቱና በአንፀባራቂነቱ ሊታወስ የሚችል ነው። ከዚህ ልምድ በመውሰድ የአንድነት አባላት ዴሞክራሲያዊ በሆነና በሰለጠነ መንገድ መሪዎቻቸውን መምረጥ የሚችሉበት ሁኔታ ከፈጠሩ፤ የሌሎች ፓርቲ አመራር አባላትም በተመሳሳይ መንገድ መሄድ የማይችሉበት ምንም ዓይነት ምክንያት የለም። ስለዚህ በአንድነት ፓርቲ ውስጥ የተሳካ የተሀድሶ አብዮት ማካሄድ ከቻልን ቀጥሎ በመኢአድ፣ በመድረክ፣ በአረና፣ በኦፌኮ፣ በደቡብ ህብረት፣ በኢዴፓና በአጠቃላይ በተቃውሞ ጎራ ባሉ ኃይሎች ሁሉ ይሄ የለውጥ እንቅስቃሴ እንዲቀጣጠል እድል የሚፈጥር ነው የሚሆነው። በመሆኑም ውህደቱ ለጊዜው ቢጨናገፍም በአንድነት አባላትና ደጋፊዎች ዘንድ የተጀመረውን የትግል መነሳሳት መቀዝቀዝ የለበትም። ይሄ መነሳሳት ፓርቲውን በአዲስ መንፈስና በአዲስ ፖለቲካዊ አካሄድ ለማስኬድ በሚያስችል መልኩ ልንጠቀምበት እንችላለን። ባለበንት እንድንረግጥ ከሚያደርገን ያረጀና ያፈጀ ፖለቲካዊ አሰራር ፖለቲካው ይላቀቅ ዘንድ የለውጥ ኃይሉ በአንድነት ውስጥ የፓርቲው ህግና ስርዓት በሚፈቅደው መሰረት የተሀድሶ እና የለውጥ እንቅስቃሴ ማካሄድ መቻል አለበት። ይሄ የለውጥ እንቅስቃሴ የፓርቲውን አንድነትና ጥንካሬ አስጠብቆ አሸናፊ ሆኖ የሚወጣ ከሆነ በሁሉም የተቃውሞ ጎራ ውስጥ የሚቀጣጠል፤ በእንቅልፍና በድንዛዜ ውስጥ ያሉት ፓርቲዎች ሁሉ የለውጥና የፀደይ አብዮት ውስጥ የሚገቡበት ሁኔታ እንዲፈጠር ምክንያት የሚሆን ነው።


ይሄ ብቻ አይደለም፤ እውነተኛ የተቃውሞ ኃይሉ ወደ አንድ ጠንካራ ዴሞክራሲያዊ አውራ ፓርቲነት የሚለወጥበት ሁኔታ እንዲፈጠርም ምክንያት ይሆናል። በሁሉም ፓርቲዎች ያለው የየራስ ፓርቲ ጥግ አስይዞ ፖለቲካውን ባለበት እንዲረግጥ እያረገ ያለው ፖለቲካዊ አሰራርና ኋላቀር አካሄድ መለወጥና ከስሩ መንቀል ከተቻለ፤ የአንድ አውራ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ ውልደት እውን የሚሆንበት ጊዜ ሩቅ አይሆንም። ከዚያ በኋላ አንድነት፣ መኢአድ፣ ሰማያዊ፣ ኦፌኮ፣ አረና ወዘተ የሚል ሳይሆን አንድ የተጠናከረ የተቃውሞ ጎራ መንፈስ ብቻ ነው የሚኖረው። ትግሉም በአምባገነኑ ገዥው ፓርቲ እና በዴሞክራሲያዊው አውራ ፓርቲ መካከል ብቻ ስለሚሆን በሰላማዊ ትግል ህዝባዊ ማዕበልና ንቅናቄ ለመፍጠር የተመቻቸ ነው የሚሆነው። የህዳሴው አብዮት በተቃውሞ ጎራ መካሄድ አለበት ሲባል፤ የተቃውሞ ጎራው በውህደትም ይሁን በሌላ መንገድ (ከየፓርቲው እየፈረሰ የተሻለ ወደ ሚለው ፓርቲ በመግባት) ወደ አንድ የለውጥ ኃይልነት ይሰባሰባል፤ ይደራጃል። ከዚያ ኋላ በጠቅላላ በሀገሪቱ የህዳሴ አብዮት እንዲካሄድና እውን እንዲሆን ማደርግ የሚከብድ አይሆንም። እንዲህ በተበታተነ ሁኔታ ከተገባ ግን መጨረሻው ያው እንደተለመደው ውድቀት ነው የሚሆነው ነው።
የተቃውሞ ፖለቲካ የለውጥ እና የመነሳሳት ሰፈር፣ የአዲስ ፖለቲካዊ አስተሳሰብ መንፈስ ጎራ መሆን አለበት እንጂ በተለያዩ ጊዜያትና ሁኔታዎች የከሰሩና የከሸፉ ፖለቲከኞች ማጠራቀሚያና መደበቂያ ዋሻ መሆን የለበትም። በራስ ውስጥ የህዳሴ አብዮት ማካሄድ ወሳኝ ቅድመ ሁነት የሚሆነው፣ በፖለቲካው ጎራ እየተስተዋለ ያለው አባታዊነት፣ ቡድናዊነትና ራዕይ አልባነት ይቀየር ዘንድ ነው። ለዚህ ደግሞ በመጀመርያ የፓርቲ አባላት በፓርቲያቸው ውስጥ ያላቸው መብት እኩል መሆኑ፤ ከየትኛውም የፓርቲያቸው አባልና አመራር ጋር የሚኖራቸው ማንኛውም ዓይነት ግንኙነትም በእኩልነትና በነፃነት መርህ ላይ የተመሰረተ መሆኑ ታውቆና ተረጋግጦ ኋላቀርና ፊውዳላዊ ከሆነው የጌታና የሎሌ ዓይነት ግንኙነት ነፃ መውጣት አለባቸው። ከዚህም ባሻገር ፖለቲካ ማለት የአንድን ግለሰብ ወይም የተወሰነ ቡድን ምንዝር ሆኖ መኖር አድርገው የሚያስቡ አባላት ካሉ በተገቢው ሁኔታ ማሰልጠንና ማስተማር ያስፈልጋል። በተቋውሞ ፖለቲካ ውስጥ ያለው ትልቁ ችግር የዴሞክራሲ እና የሌበራሊዝም ባህል ጠንቅቆ ያለማወቅ፤ በአጠቃላይ ደግሞ የፖለቲካ እውቀት ማነስ ነው። ስለዚህ ይሄ ሁኔታ መቀየር አለበት፤ ይሄ የሚቀየረው ደግሞ ለአባላትና ለደጋፊዎች ተደጋጋሚ የሆነ ስልጠና መስጠት፤ የክርክርና የውይይት መድረኮች በማዘጋጀች ተመሳሳይና ተቀራራቢ የሆነ ፖለቲካዊ አቅምና ራዕይ መፍጠር ሲቻል ነው። ከዚህም በተጨማሪ በተቻለ አቅም የጥናትና የንባብ ማዕከላት በማቋቋም በፅንሰ ሀሳብ እና በፖለቲካዊ እውቀት የታነፁ ጠንካራ አባላትና ደጋፊዎች እንዲኖሩ በማድረግ ፖለቲካዊ ትግሉ በብቃትና በጥበብ ለመምራት የሚያስችል አቅምና ሁኔታ መፍጠር ይቻላል።


አሁን ባለው የሀገራችን ነባራዊ ሁኔታ የፓርቲ ፖለቲካ ብቻውን ብዙም አዋጪ አይደለም፤ ትግሉ ወደ ህዝባዊ ማዕበልና ንቅናቄ መቀየር ካለበት ሰፋ ያለ መዋቅር መፍጠር ያስፈልጋል። ይሄ ህዝባዊ ማዕበልና ንቅናቄ ደግሞ አሁን ባሉት ድኩማን ፓርቲዎች ሊመራ የሚችል ነገር አይደለም። ሲጀመር በየፓርቲዎቹ ያሉት መሪዎች ከፍተኛ የግል የስልጣን ጥም ያለባቸውና በደመነ ነፍስ ፖለቲካውን መምራት የሚፈልጉ፤ ራዕይ አልባ መሪዎች ናቸው። በመሆኑም አሁን ልናካሄደው እያሰብነው ያለውን ፍፁም ሰላማዊ የሆነ፣ ዘመናዊ የለውጥና የህዳሴ እንቅስቃሴ ለመምራት አቅም አላቸው ተብሎ የሚታሰብ አይደለም። እኔ በበኩሌ በፕሮፌሰር በየነ ጴጥሮስ፣ በዶ/ር መራራ ጉዲና፣ በኢንጂነር ግዛቸው ሽፈራው እና በመሳሰሉት የስልሳው ትውልድ ቅሪቶች ትግሉ ተመርቶ ለውጥ ይመጣል ብዬ አላስብም። ሰላማዊ ትግሉ ለውጥ እንዲያመጣ ከፈለግን ፖለቲካው ላለንበት ዘመን በሚመጥኑ ጠንካራና ቆራጥ ሰዎች መመራት አለበት። የአንዷለም አራጌ፣ የናትናኤል መኮነን፣ የሀብታሙ አያሌው፤ የዳንኤል ሽበሺ ፓርቲ ከፖለቲካዊ እስር ይቅርታ ጠይቆ በተፈታ ሰው ሊመራ የሚችለው እንዴት ነው! አንዷለም አራጌ ከስርዓቱ ጋር ተደራድሮ፣ ይቅርታ ጠይቆ መውጣት፣ ከዚያም ሊቀመንበር መሆን አቅቶት እኮ አይደለም! ዳገቱ ላይ የሚቆም ሰው በመጥፋቱ እኔ እስኪ መስዋዕት ሆኜ ምሳሌ ልሆን ብሎ ነው፤ በእስር ቤት መከራና ግፍ እየተቀበለ ያለው። ለእነዚህ ጀግኖች እያስተላለፍነው ያለው መልዕክት እኮ ትክክል አይደለም። በግፍ ያሰራቸውን ሰርዓት ይቅርታ ጠይቀው እንዲወጡ የሚያደርግ ነው። ለዚህ ነው ለመታሰርና ለመሞት የተዘጋጁ አባላት በተመሳሳይ ሁኔታ ለመታሰርና ለመሞት በተዘጋጀ መሪ መመራት አለባቸው የምለው።


እኔ ለኢንጂነር ግዛቸው እንደመሪዬም፣ እንደ አንድ የሀገሬ አንጋፋ ፖለቲከኛም ትልቅ አክብሮት ነው ያለኝ፤ ለፕሮፌሰር በየነ ጴጥሮስ እና ለዶ/ር መራራ ጉዲናም እንዲሁ ተመሳሳይ የሆነ አክብሮት አለኝ። በጊዚያቸው ያደረጉት ተጋድሎም ቢሆን እጅግ የሚመሰገን ነው። በተለይ ዶ/ር መራራ ጉዲና በኦሮሞ ህዝብ ፖለቲካዊ ትግል ላይ የራሳቸው አሻራ ያኖሩና በዓይነቱ የተለየ የትግል መንገድ ያሳዩ ትልቅ ሰው ናቸው። ለዚህ አበርክቷቸው ትልቅ ምስጋና ሊሰጣቸው የሚገባ ነው። ነገር ግን እነዚህ አንጋፋ የፖለቲካ መሪዎች ባለፉት ሀያ አመታት ትግሉን መርተው የሚፈለገው ያህል አመርቂ ለውጥ አላመጡም በሚለው መሰረታዊ ነገር ላይ ማትኮር ያሻል።


ስለዚህ ከእኛ ወዲያ ላሰር ከሚል የግል ስሜትና ፍላጎት ወጥተው እስኪ ደግሞ ከታች ያሉት አዳዲስ ትውልዶች ይምሩትና እንየው፤ እኛ ደግሞ አጠገባቸው ሆነን ምክርና ድጋፍ እንስጥ ወደሚል በጎ ሀሳብ መምጣት መቻለ አለባቸው። በእውነቱ እንነጋገር ከተባለ፣ ኢንጂነር ግዛቸው በጣም ትልቅ ሥራ ሰሩ የሚባለው ተመልሰው ወደ መሪነት ሲመጡ ካቢኒያቸው ብቃት ባላቸው ታጋዮችና ምሁራን እንዲዋቀር ማድረጋቸው ነው። ተክሌ በቀለ፣ በላይ ፍቃዱ፣ ስዩም መንገሻ፣ ዳንኤል ተፈራ፣ ኢንጂነር ዘለቀ ረዲ፣ ሰሎሞን ስዩም፣ ሀብታሙ አያሌው፣ ዳዊት አስራደ፣ ዘካርያስ የማነ ብርሃን፣ አለነ ማህፀንቱንና ሌሎችም ያየን እንደሆነ ሥራቸውን ለማመስገን እንገደዳለን። በእድሜም ቢሆን በወጣትነት እድሜ ላይ ካሉት ጀምሮ እስከ ጎልማሳ እድሜ ድረስ ያሉ ናቸው። ይሄ በራሱ ፈር ቀዳች የሚባል ዓይነት ነው። ችግሩ ግን እንዲህ ዓይነቱ ጠንካራ ስብስብ የያዘ ካቢኔ ለራሳቸው ለኢንጂነሩም ቢሆን ፈታኝ የመሆኑ ነገር ነው። እንዲህ ያለ በልምድ፣ በትምህርትና በእውቀት የተጠናከረ ካቤኔ መሪ መሆን ባንድ በእኩል መታደል ሲሆን፣ በሌላ በእኩል የግል ስሜትና የክብር ጉዳይ የሚቀድም ከሆነ ደግሞ የዚያው ያህል ስራዎች እንዲበላሹ፣ አብሮ የመስራትና የመተጋገዙ መንፈስ እንዲዳከም ምክንያት ይሆናል።


በመሰረቱ ለውጥ የምንፈልገው በፖለቲካው ዘገምተኝነት እጅግ በጣም ስለተሰላቸን ነው። ለውጥ እንፈልጋለን፤ ፖለቲካው ከገባበት የአዙሪት ሽንፈት የሚላቀቅበት መንገድ እንፈልጋለን፤ ስለዚህ እነዚህ አንጋፋ ፖለቲከኞች እንቅፋት መሆን የለባቸውም፤ ወይም ራሳቸውን ለመለወጥና በተገቢው ሁኔታ ትግሉን ለመምራት ቆርጠው መነሳት አለባቸው፤ ወይም አቅሙ ላላቸው ማስተላለፍ መቻል አለባቸው። ካሁን በፊት እንዳልኩት የፖለቲካ ብቃት በእድሜ ማነስም ሆነ መብዛት የሚገናኝ አይደለም። ችግሩ ያለው የቀደመው ትውልድ ትንታጉና ብቃት የነበረው ሁሉ በልዩ ልዩ መንገድ ማለቁ ነው። አሁን የዚያ ትውልድ አመዱ ብቻ ነው የቀረው ማለት ይቻላል፤ ያሉትም ቢሆኑ በእድሜ መግፋት፣ በኑሮ ጫና እንዲሁም በዴሞክራሲያዊ ባህል እጥረት ምክንያት አሁን ያለውን ትግል ለመምራት ይቸገራሉ የሚል እምነት ነው ያለኝ። ስለዚህ ፖለቲካዊ ፍላጎትና መሪ የመሆን ምኞት ካላቸው፤ ቢያንስ በዴሞክራሲያዊና በሰለጠነ መንገድ የምናደርገውን የለውጥ ትግል እነርሱም በተመሳሳይ ሁኔታ በሰለጠነ መንገድ መታገልና መወዳደር ይችላሉ፤ በፖለቲካው መስክ እስካሉ ድረስ መብታቸውም ነው። ነገር ግን ኋላ ቀር ከሆነው የጠልፎ መጣል ሴራ እና የፍረጃ ፖለቲካ መውጣት መቻል አለባቸው።


ከሁሉም ነገር በፊት ለሀገርና ለህዝብ ነው መታሰብ ያለበት። በፖለቲካው ትግል መስክ ያገናኘንም ዋነኛው ምክንያት ይሄ የሀገር እና ህዝብ ጉዳይ ነው። የህዳሴው አብዮት ማካሄድ አስፈላጊ የሚሆነው የተወሰነ ቡድን ፖለቲካዊ ፍላጎት ለማርካት ሳይሆን በጠቅላላ ሀገርና ህዝብ ለመለወጥ፤ የህግ የበላይነት የሰፈነበት የተደላደለ ህገመንግስታዊ ስርዓት ለማምጣት ነው።


በሌላ መልኩ ካየነው ደግሞ፣ የተቃውሞ ጎራው የተሳካ ተሀድሶ ማካሄድ ከቻለ፣ በገዥው ፓርቲ ቤት ውስጥም ተመሳሳይ ሁኔታ እንዲፈጠር ምክንያት ሊሆን የሚችል ነው። ከዚህም ባሻገር ትልቅ የሆነ የአስተሳሰብና የአተያይ ለውጥ እንዲመጣ የሚያደርግ ነው። ከድል በኋላ ግንባሩን የተቀላቃሉ ወጣቶችና ምሁራን “እኛስ ከማን እናንሳለን? ለምን እውነተኛ የሆነ የተሀድሶና ለውጥ እንቅስቃሴ አናደርግም?” ብለው እንዲያስቡና እንዲነሳሱ ሊያደርጋቸው ይችላል። ይሄ ከሆነ ደግሞ ብዙ ነገር ተቃለለ ማለት ነው። ታንክና መድፍ እያንጋጋ ከመጣው አሮጌ አመራር ይልቅ በብዙ መልኩ እኛ የሚመስሉትን አዲሶቹ የኢህአዴግ ትውልዶች ጋር መነጋገርና መግባባት የሚቻል ነው የሚመስለኝ። ሲጀመር እነርሱ ስልጣን ቢያጡም እንዲህ እንሆናለን፣ እንታሰራለን፣ ይበቀሉናል የሚሉበት ሁኔታ የለም። ስልጣን ቢያጡ እንኳ ሰርተው ወይም ነግደው የሚኖሩበት ሁኔታ ነው የሚኖረው። እንዲያውም በስርዓቱ አማካይነት የተሻለ ኢኮኖሚያዊ አቅምና የትምህርት እድል እንዲኖራቸው የተደረገ በመሆኑ እውነተኛና ዴሞክራሲያዊ የሆነ የነፃ ገበያ ስርዓት ሲሰፍን በተሻለ ሁኔታ ተጠቃሚ ለመሆን ከሌላው የተሻለና የተደራጀ አቅም ያላቸው ይሆናሉ።


ከፖለቲካዊ ተፅዕኖ ገለልተኛ የሆኑ ተቅዋማትና የህግ የበላይነት የሰፈነበት የተደላደለ ስርዓት እስካለ ድረስ ሰዎች በነበራቸው ፖለቲካዊ አመለካከት የሚጠቁበት ሁኔታ ፈፅሞ አይኖርም። ለዚህ ነው፤ እኔ የተሻለ አስተሳሰብና ፖለቲካዊ ባሀል በማምጣት በገዥው ፓርቲ ጥላ ስር ያሉትን ዜጎች ሳይቀር አዎንታዊ ተፅዕኖ በመፍጠር የዚህ የህዳሴው አብዮት አካል እንዲሆኑ ማድረግ እንችላለን የምለው። በመሆኑም ይሄ የለውጥ ፕሮጀክትና የተሀድሶ እንቅስቃሴ እንዲሁ በቀላሉ የሚታይና የሚታለፍ መሆን የለበትም። በዚህች ሀገር ያለው ፖለቲካዊ ባህል እንዲለውጥ የምንፈልግ ሁሉ ሀሳቡ ማስፋት ማጠናከር ብሎም ወደ መሬት በማውረድ ለተግባራዊነቱ ቆርጠን መነሳት፣ በተገቢው ሁኔታም መንቀሳቀስ መቻል አለብን። በዚህ መንገድ ከታገልን ለሁላችንም የምትበቃ፤ የተሻለችና ሁሉም ዜጎቿ ያለልዩነት የሚኮሩባት ሀገር እንድትኖረን ማድረግ እንችላለን። ስለዚህ የህዳሴው አብዮት በዚህ ሁኔታና እይታ ነው መቃኘት ያለበት የሚል እምነት ነው ያለኝ።

 

የፀጥታ ሃይሎች በጭፍን ታዛዥነት የሚጥሷቸው መሰረታዊ መርሆች

$
0
0

ድምፃችን ይሰማ!

muslim 2በሃገራችን ኢትዮጵያ ህገ መንግስት መግቢያ ላይ በግልፅ እንደሰፈረው ሃገራችንን እንዲመራ የሚመሰረተው መንግስት በኢትዮጵያ ህዝቦች ነፃ ፍላጎት፣ በህግ የበላይነት እና በህዝቦች ፈቃድ የህዝቡን የጋራ ጥቅም፣ መብት እና ነፃነት እንዲያስከብር የሚመሰረት የፖለቲካ ተቋም ነው፡፡ ይህ የፖለቲካ ተቋምም ህዝባችንን በትጋት እና በህግ በታቀፈ አካሄድ እንዲያገለግል ተደርጎ የተመሰረተ ሊሆን እንደሚገባው ህገ መንግስቱ በጥብቅ ያሳስባል፡፡ በመቀጠልም ህገ መንግስቱ በአንቀፅ 8 ንዑስ አንቀፅ 1 ህዝቦች የሃገራችን ኢትዮጵያ ሉአላዊ ስልጣን ባለቤቶች መሆናቸውን ረጋግጣል፡፡ ከዚያም በመቀጠል በአንቀፅ 9 ንዑስ አንቀፅ 1 ከህገ መንግስቱ ጋር የሚቃረን ማንኛውም የውስጥ ደንብም ይሁን መመሪያ ውድቅ መሆን ያለበት መሆኑን በማስገንዘብ ያሰፈረ ሲሆን በአንቀፅ 9 ንዑስ አንቀፅ 2 ደግሞ ማንኛውም የመንግስት አካልም ሆነ የፖለቲካ ድርጅት ለህገ መንግስቱ ተገዢ መሆን እንዳለበት በጥብቅ ያስገነዝባል፡፡

እንግዲህ በህገ መንግስቱ መግቢያና በአንቀፆቹ የተገለፁትን ሃሳቦች ጠቅለል ባለ መልኩ ከተመለከትናቸው በሃገራችን የሚመሰረተው መንግስት ህዝብን ለማገልገል የሚመሰረት ተቋም መሆኑን እና የመንግስት አካል ሆነው የሚፈጠሩ ማናቸውም ክፍሎች ለህገ መንግስቱ ተገዢዎች፣ እንዲሁም ህገ መንግስቱን በተግባር ለመተርጎም የሚፈጠሩ መሆን እንዳለባቸው እንረዳለን፡፡ በተቃራኒው ህገ መንግስቱን የማፋለስ እና የመርገጥ መብት የሌላቸው መሆኑንም እንገነዘባለን፡፡ በተጨማሪም በማንኛውም የመንግስት ተቋማት ተቀጥሮ የሚሰራ ግለሰብ ዋነኛ እና ከፍተኛ ኃላፊነቱ ህዝብን ማገልገል እና የህዝቡን ጥቅም እና ነፃነት መጠበቅ መሆኑን እንረዳለን፡፡

ከዚህ መሰረታዊ ሃሳብ ከተነሳን በመንግስት ተቋማት ውስጥ በመቀጠር የህዝብን መብት እና ነፃነት የሚጋፉ፣ ወይም የማህበረሰባቸውን መብት እና ነፃነት የሚገፍ ማንኛውንም ትዕዛዝ የሚቀበሉ፣ የሚፈፅሙ እና የሚያስፈፅሙ አካላት ቢያንስ የሚከተሉትን ሶስት መሰረታዊ የህገ መንግስት ጥሰቶች መፈፀማቸውን ልንገነዘብ እንችላለን፡-

1. አንድ ግለሰብ በሃገራችን ሉዓላዊው አካል እና ከፍተኛ የስልጣን ባለቤት ህዝብ መሆኑን እያወቀ የህዝብን ደህንነት እና ነፃነት የሚጋፉ ድርጊቶችን እንዲፈፅም የሚሰጠውን ትዕዛዝ መቀበሉ እሱም የህዝቡ አካል ነውና በቅድሚያ የራሱ ህገ መንግስታዊ መብት እንዲረገጥ በፍቃደኝነት የተቀበለና ለህገ መንግስቱ ክብር የሌለው መሆኑን ያረጋግጣል፤
2. ግለሰቡ የህብረተሰቡን መብት የሚጥሱና ነፃነቱን የሚያቃውሱ ድርጊቶችን እንዲፈፅም ታዝዞ ድርጊቱን ከፈፀመ የወገኖቹን የህገ መንግስት መብት የሚጥስ እና የሚረግጥ በመሆኑ ዳግም ህገ መንግስቱን ይጥሳል፤ ይረግጣል፤

3. ህገ መንግስታዊ መብታችን ተጥሷል በማለት ተቃውሞ የሚያሰሙ የህብረተሰብ ክፍሎችን ለማፈን እና ይህን መብታቸውንም ለመግፈፍ የተሰማራ ከሆነ በሶስተኛ ደረጃ ህገ መንግስቱን ይጥሳል፤
በመሆኑም እያንዳንዱ ዜጋ በሚያደርገው ድርጊት ዛሬ መንግስትን በታማኝነት ሲያገለግል ድርጊቱ ከህገ መንግስቱ ጋር የሚጣጣም እና የህገ መንግስቱን መንፈስ የተከተለ መሆን አለመሆኑን የማጣራት ግዳጅ ያለበት ሲሆን ይህንን ችላ ብሎ ህገ መንግስቱን የሚፃረሩ ድርጊቶችን መፈፀሙ ነገ የህግ የበላይነት በሃገሪቱ ሲሰፍር እና እኛ የኢትዮጵያ ህዝቦች መብታችንን በፍትሃዊ ፍርድ ቤት የምናከብርበት ወቅት ሲመጣ በህገ መንግስቱ መሰረት ለፍርድ የሚቀርብ መሆኑን ሊገነዘብ ይገባዋል፡፡ ይህን ከግምት በመክተት እያንዳንዱ ዜጋ ህገ መንግስቱን ተገንዝቦ የራሱን መብት አክብሮ የሌላውን ወገኑን መብት እንዲያከብር አጥብቀን በወገናዊነት ስሜት እንጠይቃለን፡፡ ታማኝነት ለህግ እና ለህገ መንግስቱ እንጂ ራሳቸውን ‹‹የህዝብ ተወካዮች›› ሲሉ ሰይመው ህዝብን ለመርገጥና መብት ለመግፈፍ ለቆሙ ጥቂት አምባገነኖች አይደለም! የአምባገነኖች አገልጋይና መሳሪያ በመሆን ካገለገሉ በኋላ ‹‹ህዝብ ላይ በደል የፈጸምኩት በእነሱ ትዕዛዝ ነው›› ማለት ከተጠያቂነት አያድንም!
ህገ መንግስቱን ማክበር እና ማስከበር ህዝባዊ ሀላፊነታችን ነው!!!
ትግላችን እስከድል ደጃፎች በአላህ ፈቃድ ይቀጥላል!

የሕዝብን የነፃነት ትግል ማስቆም ፈጽሞ አይቻልም (ሸንጎ)

$
0
0

ነኅሴ 10 ቀን 2006 Augest 16, 2014
shengoየአንድነት ፓርቲና የመኢአድ አመራሮችና አባላት ድርጅቶቻቸውን ለማዋሃድና የሚያደርጉትን ሰላማዊ የነፃነት ትግል ወደ ከፍተኛ ደረጃ ለማሸጋገር እንቅስቃሴ ከጀመሩ በርካታ ወራት እንዳስቆጠሩ
የሚታወቅ ነው። የሀገሪቱ አፋኝ ህግ በሚፈቅደው መሠረት በጥሞና ደረጃ በደረጃ ተንቀሳቅሰው የውህደቱን ሂደት ለማጠናቀቅ የሚያስችለውን የጋራ ጉባኤ ለማካሄድ ጥቂት ቀናት ብቻ ሲቀር የህወሓት/ኢህአዴግ መሣሪያ የሆነው “የምርጫ ቦርድ” ሰበብ በመፍጠር የታቀደው የውህደት ጉባኤ እንዳይካሄድ አድርጓል። ይህን እጅግ አሳፋሪና ተራ አፍራሽ ተግባር ሸንጎ አጥብቆ ያወግዛል።—–[ሙሉውን ለማንበብ እዚህ ይጫኑ]———

ኢትዮጵያውያን በሳዑዲ አረቢያ ሪያድ ከተማ ሲታፈሱ አመሹ

$
0
0

saudi ethiopia 1

saudi ethiopia 2

saudi ethiopia 3

saudi ethiopia 4

saudi ethiopia 5
ለዘ-ሐበሻ የዘገበው ኢትዮጵያ ሃገሬ ጅዳ በዋዲ

የሳውዲ አረቢያ መንግስት ያለመኖሪያ ፈቃድ የሚኖሩ ህገወጥ ውጭ ሃገር ዜጎች ሃገሪቱን ለቀው እንዲወጡ የሚገልጸውን መመሪያ ተግባርዊ ለማድረግ የፀጥታ ሃይሉ በወሰዱት እርምጃ ከ1 መቶ 80 ሺህ በላይ እትዮጵያውያን ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ከቤት ንብረታቸው ተፈናቅለው የሳውዲን ምድረ ለቀው ወደ ሃገር መመለሳቸው ይታወሳል። ይህ በዚህ እንዳለ የሳውዲ ከስደት ተመላሽ ወገኖችን መልሷ የማቋቋም ከፍተኛ ሃላፊነት የተጣለበት የኢትዮጵያ መንግስት ሁሉንም ለማድረግ በተደጋጋሚ ቃል ቢገባም በወቅቱ የዓለምን ህዝብ ትኩረት ስቦ የነበረው የኢትዮጵያውያኑ ጉዳይ እስኪረጋጋ የውጭ ጉዳይ ሚንስትሩ ዶ/ር ቴድሮስ አድሃኗም ከስደተኛው ጋር ፎቶ በመነሳት በኢቲቪ ሲሰራጭ ከነበረው ሰፊ የዜና ሽፋን ባሻገር ስደተኛው ምንም አይነት ማቋቋሚያም ሆነ ድጋፍ እንዳላደረጉላቸው ይነገራል። በተለይ የስደት አለም ህጻናት ልጆቻቸውን ታቀፈው ለሃገር የበቁ እናቶች ለጎዳና ተዳዳሪነት የተዳረጉበት አስዛኝ ታሪክ የአብዛኛውን ኢትዮጵያዊ ሆድ አላውሷል ። መንግስት በወቅቱ አዲስ አበባ በስደተኞቹ እንዳትጨናነቅ የስደተኞቹ ጉዳይ በየክልሉ ባለስልጣናት የታያል በሚል ሽፋን በመቶሺህ የሚቆጠረውን ስደተኛ በየጉራጉሩ ወሽቆ ነገሮቹን ለማድበስበስ ቢሞክረም አብዛኛው ወገኖች በቋፍ ላይ ያለቸውን ህይወታቸውን ለመታደግ አቀም ያለው አይቀሬውን ሞት በመጋፈጥ፡ በህይወቱ ቆርጦ ሳውዲ አረቢያ ለመግባት ቀይ ባሀርን በጀልባ አቋርጧ ለዳገም ስደት ተዳርጓል።

በአንጻሩ በሰው ሃገር ወልዶ ከብዶ በወቅቱ ያገኛት በነበረች የዕለት ገቢው ከእጅ ወደ አፍ የሆነ የስደት አለም ጎጆውን አሞቆ ያለጥሪት ይኖር የነበረው አባወራ ያቺን ቀውጢ ውቅት መቋቋም ተስኖት የቤተሰቦቹን ህይወት ከወረበሎች ለማዳን ወደ ሃገሩ እግሬ አውጪኝ ቢልም ያለጠበቀው ገጥሞት የሞቀ የስደት ዓለም ትዳሩን መቅኔ ያሳጣውን የመንፉሃው ሁከት እየረገመ በገዛ ሃገሩ ሰማይ ተድፍቶበት ለልጆቹ የዕለት ጉርስ ዳቦ መግዣ አጥቶ የህጻናቱን ስቃይ እና መከራ ላለማየት እግር ወዳ መራው ሲኳተን በረሃ በልቶት እደወጣ የቀረውን ከሳውዲ ስደት ተመላሽ ኢትዮጵያዊ ቤት ይቁጠረው ። ይህ ባለበት ሁኔታ የሳውዲ ፀጥታ ሃይሎች በዛሬው ዕለት ባደረጉት የተጠናከረ የቤት ለቤት ፍተሻ ከ1 ሺሕ በላይ ህገ ወጥ ሰዎች በቁጥጠር ስር መዋላቸውን የሚናገሩ ምንጮች ከግማሽ በላይ የሚሆኑት ኢትዮጵያውያን መሆናቸው ጉዳዩን የበለጠ አሰደንጋጭ ያደረገዋል ። የፀጥታ ሃይሉ ከህብረትሰቡ በሚቀርብላቸው መረጃ መስረት ዘመቻውን በቀጣይነት በሪያድ ከተማ በተለምዶ ነሲም አል ሃማም እና ጉቤራ እይተባሉ የሚጠሩ መንደሮችን በማማከል አጠናክረው እንደሚቀጥሉ ከውስጥ አዋቂ ምንጮች ማረጋገጥ ተችሏል።። ከአንድ ወር በፊት በሪያ ድ ከተማ የአንድ ወህኒ ቤት ግርግዳ ደምርሰው ኢትዮጵያውያኑን ጨምሮ ቁጥሩ በወል የማይታወቅ እስረኞች ማምለጣቸው ይታወሳል ።

በዛሬው ዕለት መንፉሃ ውስጥ በተካሄደው የቤት ለበቤት ፍተሻ በኢትዮጵያውያን ላይ ስለደርሰ እንግለት ወደ ሪያድ የኢትዮጵያ ኤንባሲ ስልክ በመደወል ለማረጋገጥ ባደረኩት ጥረት አንድ ስሜ እንዳይገለጽ ያሉ ዲፕሎማት የቤት ለቤት ፍተሻው በኢትዮጵያውያኖች ላይ ብቻ ያነጣጠረ እንዳልነበረ ገልጸው በዘመቻው ወቀት ከፍተኛ የሳውዲ ፀጥታ ሃይል መኮንኖች እና የመዲናይቱ ባለስልጣናት የቀርብ ክትትል እና ቁጥጠር ያደርጉ እንደነበር በማውሳት እርምጃው በባህር የመጡ የመኖሪያ ፈቃድ በሌላቸው ህገወጥ የአካባቢው ነዋሪዎች ላይ ብቻ ያነጣጠረ እና በየትኛውም ዜጋ ላይ ምንም አይነት እንግለት ያለተፈፀመ ጥናቃቄ የተሞላበት ዘመቻ እንደነበር አረጋግጠናል ብለዋል ።በማስከተል ትላንት የሻኞቸውን ኢትዮጵያውያን ደግማችሁ ዛሬ ስትሸኙ ምን ይሰማችሃል ላልኳቸው ጥያቄ ምላሽ ሳይሰጡኝ ተሰናብተውኛል። ዛሬ ማለዳ መንፉሃ ውስጥ በሳውዲ ፀጥታ ሃይሎች ተካሄደ በተባለው የቤት ለበቤት አፈሳ ዙሪያ ተጨማሪ መረጃዎችን ከአካባቢው ነዋሪዎች እና ወህኒ ከሚገኙ ወገኖች መረጃ በማሰባሰብ በሰፊው ለመዘገብ የማደርገው ጥረት ይቀጥላል ።

በኢትዮጵያውያን ላይ በሳዑዲ አረቢያ የተፈጸመው የአፈሳ ተግባር (ተጨማሪ ፎቶዎች)

$
0
0

(ዘ-ሐበሻ) ከወራት በፊት በሳዑዲ አረቢያ ኢትዮጵያውያኑን እስከመግደልና አስገድዶ እስከመድፈር የደረሰ በደል ሲደርስባቸው ሁላችንም አደባባይ ወጥተን ጮኸን፤ አልቅሰን ነበር። ትንሽ ጋብ ያለ መስሎ የነበረው ይህ ስቃይ በመቀጠል ዛሬ ኢትዮጵያውያኑ ሲታፈሱ፣ ሲሰቃዩ ውለዋል። ቀደም ባለው የዘ-ሐበሻ ዜና እወጃ ስላለው ሁኔታ የዘገብን ሲሆን ተጨማሪ አፈሳውን የሚያሳዩ ፎቶዎችን አግኝተናል ተካፈሉን። በሃገር ቤትም በስደትም በወገኖቻችን ላይ የሚደርሰው ስቃይ የሚበርደው መቼ ይሆን?
ethiopian in saudi 1

ethiopian in saudi 2

ethiopian in saudi 3

ethiopian in saudi 4

saudi ethiopia 5

saudi ethiopia 4

saudi ethiopia 3

saudi ethiopia 2

saudi ethiopia 1

የዘንዶ ሱባዔ? –ከቀሲስ አስተርአየ ጽጌ

$
0
0

Kesis Asteraye Tsige Responds to Abune Mathias (Audio)nigatuasteraye@gmail.com
ነሐሴ ፳፻፮ ዓ.ም.

ማሳሰቢያ:- የዚህን አመት የፍልሰታን ሱባዔ በመጨረስ ላይ ነን። ይሁን እንጅ በዘንድሮዋ ሱባዔ በቨርጅንያ የተከሰተው ነገር የዘንዶን ሰባዊዔ የሚያንጸባርቅ ነው። ስለዚህ ይህች ጦማር የዚህን አመት ሱባዔ ለማስታወስ ተዘጋጅታ የቀረበች ናት።

ሙሉውን ለማንበብ እዚህ ይጫኑ

የልደታ ፍርድ ቤት 19ኛ ወንጀል ችሎት የዞን9 ጦማርያኑን እና የጋዜጠኞቹን የዋስትና ጥያቄ ውድቅ አደረገ

$
0
0
36884-zone9-bloggers4ስድስቱን የዞን ዘጠኝ አባላት ማለትም በፍቃዱ ኃይሉ፣ አቤል ዋበላ፣ ማኅሌት ፋታሁን፣ ናትናኤል ፈለቀ፣ ዘላለም ክብረት እና አጥናፍ ብርሃነ እንዲሁም በሌለችበት ክሷ እየታየ ያለው በሶልያና ሽመልስ እንዲሁም በጋዜጠኞቹ ኤዶም ካሳዬ፣ ተስፋለም ወልደየስ እና አስማማው ኃ/ጊዮርጊስ በልደታ 19ኛው የወንጀል ችሎት ዛሬ ጠዋት የተሰየመ ሲሆን ከሙስሊም ኮሚቴ አመራሮች ጋር በአንድ ችሎት እንዲታደሙ በመደረጉ የታሳሪዎችን ቤተሰቦችም ሆነ ወዳጆችን ለማስተናገድ ቦታ የለም በሚል ለጋዜጠኞች ብቻ የፍርድ ሂደቱ እንዲታይ በፖሊስ ተፈቅዶ ነበር፡፡
በሌለችበት የተከሰሰችው ሶልያና ሽመልስ መጥሪያ በጋዜጣ መውጣቱን ፍርድ ቤቱ ያረጋገጠ ሲሆን የዋስትና መብትን በተመለከተ በዛሬው ዕለት ተሰይሞ የነበረው ችሎት በጸረ ሽብር አዋጁ መሰረት በአንቀጽ 3 የሽብር ተግባራት ተብለው ከተዘረዘሩት ውስጥ አንድም ወይም ሁለትም ከዚያም በላይ ወንጀል የፈጸመ መሆኑ ወይም ለመፈጸም ያቀደ ለመሆኑ ተገልጾ ክስ ሲቀርብ ነው በተመሰረተባቸው ክስ ዋስትናን ሊያሳጣቸው የሚችለው ብለው ጠበቆቻቸው የተከራከሩ ሲሆን ደንበኞቻቸው በአዋጁ መሰረት የሰሩት የሽብር ተግባር ክስ አልቀረበባቸውም ስለዚህ በአዋጁ ተጠቀሰ ማለት በአዋጁ መሰረት ክስ ቀርቧል ማለት ስለማይቻል የዋስትናው ጥያቄ በመደበኛ ስርዓት እንጂ በጸረ­ሽብር ሕጉ መሰረት ሊታይ አይገባም፤ በተጨማሪም አዋጁ
ዋስትና ይከለክላል ተብሎ ቢተረጎምም ከሕገ­መንግስቱ ጋር ስለሚጋጭ ዋስትና ሊፈቀድላቸው ይገባል ቢሉም፤ ፍርድ ቤቱ አንቀጽ ተጠቅሶ መከሰሳቸውን እንጂ በዚህ መከሰስ ነበረባቸው ወይም አልነበረባቸውም ብሎ ለማየት ፍርድ ቤቱ አይገደድም እንዲሁም የጸረ­ሽብር አዋጁ ከሕገ­መንግስቱ ጋር አይጋጭም ብለዋል በዚሁም መሰረት የዋስትና ጥያቄውን ውድቅ ተደርጎ ለጥቅምት 5 ቀን 2007ዓ.ም ቀጠሮ በመስጠት የዛሬው ችሎት የተጠናቀቀ ሲሆን ጠበቆቻቸውም የዋስትና ጉዳይ በተመለከተ ለጠቅላይ ፍረድ ቤት ይግባኝ እንደሚያቀርቡም ታውቋል፡፡
ችሎት ውስጥ መግባት የቻሉት ጥቂት ጋዜጠኞች እና ጉዳዩን ለመታዘብ የተገኙ ዲፕሎማቶች ብቻ ናቸው፡፡ በቦታው በመገኘት አጋርነታችሁን ላሳያችሁ ሁሉ ከፍ ያለ ምስጋናችን ይድረሳችሁ፡፡

አብርሃ ደስታ ሃብታሙ አያሌዉና እና ኤርትራ ( ግርማ ካሳ)

$
0
0

Habtamu abrhayeshiwas danielራሱን ግንቦት 7 ብሎ ከሚጠራ ድርጅት ጋር እና ከድርጅቱ ከፍተኛ አመራሮች በመገናኘት ፤ እንዲሁም ከባንክ በትዕዛዝ ብር በመቀበል የግንቦት 7 ተልዕኮና አላማ ለመፈፀም፤ ቁጥራቸው ከ60 በላይ የሆኑ ግለሰቦችን ለዚህ ጥፋት እንዲሰማሩ በማድረግ» የሚል ክስ ነው በወዲ ሃዉዜን/ትግራይ በሆነው አንጋፋ ፖለቲከኛ እና ብሎገር ላይ ክስ የቀረበው። ሌላው አንጋፋና አንደበተ ርትኡ፣ የሚሊዮኖች ድምጽ ንቅናቄ ግብረ ኃይል ሰብሳቢ፣ ሃብታሙ አያሌውም፣ «የግንቦት ሰባት ተባባሪ ነው» በሚል ነው ለመክሰስ ነው ዝግጅት እየተደረገ ያለው።

አብርሃ ደስታ እና ሃብታሙ አያሌው ፣ «ግንቦት ሰባትን ይደግፋሉ» የሚል ክስ ከቀረበባቸው፣ በተዘዋዋሪ መንገድ «ከሻእቢያ ጋር ወዳጆች ናቸው» ማለት ነው። ታዲያ የሻእቢያ ወዳጅ የሆነ ሰው፣ የኤርትራን መገንጠል ተቃዉሞ፣ ወይንም የኢትዮጵያን የባህር በር ባለቤት መከበር እንዳለበት በማስመር ይናገራል ወይ ? እስቲ የጸረ-ሽብርና የአገር ደህንነት ተብዬው ምላሽ ይስጠን !!!

ሁላችንም እንደምናውቀው፣ በኤርትራ በኩል ትግል እናደርጋለን የሚሉ ወገኖች፣ ኢትዮጵያ የባህር በር እንደሚያስፈልጋት ሊናገሩ አይችሉም። በሻእቢያ ሥር እስካሉ ድረስ ቀይ መስመር ተሰምሮላቸዋል። እነ ግንቦት ሰባቶች፣ ኦነጎች …፣ እርዳታ የሚያገኙጥ ከሻእቢያ ማእከላቼ ደግሞ አስመራ እስከሆነ ድረስ፣ «ኢትዮጵያ የባህር በር ያስፈልጋታል» ብለው የመናገራቸው ነገር ጭራሽ የማይታሰብ ነው።

ዶር ብርሃኑ ነጋ ከቃሊት እሥር ቤት ሆነው የጻፉት አንድ መጽሃፍ ነበር። መጽሀፍ ላይ ባለው የ ኤርትራ ካርታ ፣ ኤርትራ ተቆርጣለች። ሃብታሙ አያሌው የጻፈው መጽሃፍ ላይ በሚታየው የ ኤርትር ካርታ ኤርትራ አልተቆረጠችም። ሃብታሙ አያሌው፣ ምንም እንኳን ሻእቢያና ሕወሃት/ኢሕአዴግ ከመረብ በስተሰሜን እና በስተደቡብ ያለዉን ሕዝብ ከፋፍለው፣ በደም ቢያቃቡትም፣ «ሰላማዊ በሆነ መንገድ፣ ሁለቱም ወገኖች አሸናፊ በሆኑበት መልኩ፣ ወንድማማቾችን አንድ ማድረግ ይቻላል» የሚል እምነት ስላለው ነው፣ ኤርትራ ከተቀረው የኢትዮጵያ አካል ጋር የቀላቀላት። ከ23 አመታት በፊት ያለው አስቦ ሳይሆን ፣ ወደፊት የሚሆነው ታይቶት ነው። ታዲያ ይህ አይነት ፖለቲከኛ ነው የሻእቢያ አሽከር ነው ተብሎ የሚከሰሰው ?

ወደ አብርሃ ደስታ ልውሰዳችሁ። በቅርብ ጊዜ ስለ አሰብ የጻፈው አስደናቂ ጽሁፍ ነበር። «ጦርነት ፈርተን ግን ሐገራችንን አሳልፈን አንሰጥም» በሚል ርእስ፣ በአደብ ጉዳይ ላይ፣ አብርሃ ደስታ ሲጸፍ « እኛ ጦርነት አንፈልግም። ሕጋዊ ንብረታችን (ወደባችን) በሰለማዊ መንገድ እንዲሰጠን ነው የምንጠይቀው። አዎ! ጦርነት አንፈልግም። ጦርነት አንፈልግም ማለት ግን ጦርነት ከፍተን በሃይል የሌላ ሀገርና ህዝብ ንብረት አንወርም ማለት እንጂ ጦርነት ፈርተን ልአላዊ ግዛታችን (ሃብታችን) ለሌሎች ሃይሎች አሳልፈን እንሰጣለን ማለት አይደለም። ጦርነት አንፈልግም ማለት ጦርነት እንፈራለን ማለት አይደለም። አዎ! ጦርነት ስለማንፈልግ ሌሎች ህዝቦችን አንወርም። ጦርነት ፈርተን ግን እናት ሀገራችን አናስደፍርም» ነበር ያለው።

ታዲያ በምን መሰፍርትና ሚዛን ነው አቶ ሃብታሙ አያሌው እና አቶ አብርሃ ደስታ የ«ሻእቢያ ተላላኪ» የሚሆኑት ? በምን መስፈርት ነው ግንቦት ሰባቶች ሊባሉ የቻሉት ?

«ህወሓት በራሱ ኮ የሻዕቢያ ተልእኮ ለማስፈፀም በሻዕቢያ የተቋቋመ ድርጅት ነው። ህወሓት የመሰረተው ማነው? ሻዕቢያ ነው። ሻዕቢያ መሓሪ ተኽለ (ሙሴ) የተባለ ኤርትራዊ የሻዕቢያ አባል በትግራይ ለሻዕቢያ ሊያግዝ የሚችል ድርጅት እንዲያቋቁም ወደ ኢትዮዽያ ላከ። እነዚህ ህወሓት የመሰረቱ የሚባሉ ሰባት ሰዎች አሰባስቦ እንዲደራጁ አደረገ» ብሎ አብርሃ ደስታ እንደጻፈው፣ ለሻእቢያ ዉስጥ ዉስጡን የሚቆረቀረዉስ ሕወሃት አይደለችንም ? ያ ባይሆን ኖሮ ተሽቀዳድሞ የአልጀርስ ስምምነት ይፈረም ነበርን? ያ ባይሆን ኖሮ አገር ቤት ካሉ ሰላማዊ ተቃዋሚዎች ጋር አልነጋገርም እያሉ፣ የሕወሃት/ኢሕአዴጉ ዳግማዊ መለስ ዜናዊ፣ ኃይለማሪያም ደሳለኝ «ካስፈለገም አስመራ ድረስ እሄዳለሁ» ይሉ ነበርን ?

እርግጥ ነው እነዚህ ሁለቱ አንጋፋ ወጣት ፖለቲከኞች፣ ኢሳት በተሰኘው ሜዲያ ቀርበው ቃለ ምልልስ አድርገዋል። አቦይ ስብሐት ነጋ፣ አምባሳደር ቪኪ ሃደልሰን፣ ፕሮፌሰር ዶናልድ ሌቪን፣ ወንጌላዊ ዳንኤል ጣሰው ..የመሳሰሉትም በኢሳት ቀርበዋል። ታዲያ እነ አባይ ስብሐት ፣ «ኢሳት ላይ ቀረባችሁ» ተብለው ወደ ወህኒ የወረዱበት ሁኔታስ የታለ ?

በአንድ ሜዲያ መቅረብ አንድን ሰው ጥፋተኛ አያሰኘዉም። አንድ ሰው መከሰስ ካለበት፣ ሊከሰስ የሚገባው በቃለ መጠይቆቹ ዉስጥ ባለው ይዘት ነው። አቶ ሃብታሙና አቶ አብርሃ፣ ሲጽፉም ሲናገሩም በግልጽና በአደባባይ እንደመሆኑ «ይሄን ተናገረዋል.. » ተብለው የሚከሰሱበት ነጥብ ይኖራል ብዬ አላስብም። በመሆኑም አገዛዙ ፣ እነዚህ ሰላማዊ ዜጎችን ሽብርተኞች ናቸው ብሎ ማሰሩ የትም አያደርሰውም። ይህ አይነቱ ፍርድ ገምድልነትና ዜጎችን ያለ ከልካይ ማሰርና ማንገላታት መቆም አለበት።

ጄ/ል ባጫ ደበሌ በሜሪላንድ ግዛት የ350ሺህ ዶላር ቤት ገዙ

$
0
0

ጄነራል ባጫ ደበሌ

ጄነራል ባጫ ደበሌ


ከኢየሩሳሌም አርአያ

ጄ/ል ባጫ ደበሌ በአሜሪካ ሜሪላንድ ግዛት በ350ሺህ ዶላር ቤት መግዛታቸው ታውቋል። የባጫ ባለቤትና አንድ ልጃቸው እንደሚኖሩበት ሲታወቅ ልጃቸው በተርም ከ20ሺህ ዶላር በላይ እየተከፈለለት እንደሚማር ማወቅ ተችሏል።

በከፍተኛ ሙስና ውስጥ ከተዘፈቁ የመከላከያ ከፍተኛ የጦር አዛዦች አንዱ የሆኑት ባጫ ደበሌ በቦሌ ከለንደን ካፌ ፊት ለፊት ባለሁለት ፎቅ ዘመናዊ ቪላ ገንብተው እንደሚያከራዩ ይታወቃል። በኢትዮ- ኤርትራ ጦርነት ወቅት አሰብን ለመቆጣጠር ይገሰግስ የነበረውን የኢትዮጵያ ሰራዊት ከመለስ ዜናዊ በተላለፈ ትእዛዝ ግስጋሴው እንዲገታና ወታደራዊ እቅዱ እንዲኮላሽ ከፍተኛ ሚና የተጫወቱት ባጫ ደበሌ መሆናቸውን የቅርብ ምንጮች ያረጋግጣሉ።

ባጫ የአቶ መለስን “ሃሳብ” ተግባራዊ በማድረጋቸው በሙስና ሃብት ጥግ መድረስ ችለዋል ሲሉ ምንጮቹ ያክላሉ።

አዲሱ የቴዲ አፍሮ “በ70 ደረጃ”ነጠላ ዜማ ሙሉ የዘፈን ግጥም

$
0
0

በሰባ ደረጃ

ከመኮንን ድልድይ ከእንጨት ፎቁ በላይ
ሲመሽ እንገናኝ
መጣሁ አንቺን ብዬ ሳይከብደኝ እርምጃዉ
በሰባ ደረጃዉ

አዝማች፡
በሳሪያን ኮት ላይ ያንን ቀጭን ኩታ ጣል አድርጌ
በመኮንን ድልድይ ልምጣ በደረጃዉ በፒያሳ አድርጌ
በፍቅር ማነቂያዉ ዶሮ እንዳይል በከንቱ እረ አንቺን ወዶ ..(ዶሮ ማነቂያ፣ ዕሪ በከንቱ)
ክራሩን ስትሰሚ ብቅ በይ ቆሞያለሁ ከበርሽ ማዶ

ሲመሽ ወደማታ ማታ ማታ
አቤት ያንቺ ፍቅር ሲበረታ
ሲመሽ ወደ ማታ ማታ ማታ
ብቅ በይ ሲገረፍ ክራር ሲመታ

ማታ ማታ
ማታ ማታ

አምጣት ከጎኔ ትቀመጥ
እንጀራ አይቀርብም ካለወጥ
አቅፎ ገላዋን አልጠግብ ያለዉ
ማነዉ ብላችሁ ማነዉ ማነዉ?

ልቤ ልቤነዉ ልቤ እራብተኛዉ
እሏን ወዶ ሌት የማይተኛዉ
ይዉጣ ይዉጣ እግሬ ይዛል በእርምጃዉ
ከሏ አይብስም ሰባ ደረጃዉ

ዘበናይ ዘበናይ….

ሲመሽ ወደ ማታ ሁሉ ዘግቶ በሩን
ታም ታራም ሳረገዉ ብቅ በይ ክራሩን

ታም-ታራራም-ታራራም…..

ፀጉራን ተተኩሳዉ እንደ አርምዴ ሜሪ
ዘበናይ ናት ፍቅሯን በክራር ነጋሪ.

ታም-ታራራም-ታራራም…..

ሄዶ ከኮሪያ ዘማች ሲመለስ
ያወሳል ናፍቆቱን በክራሩ ድምጵ
ፍቅርሽ አስጨንቆ መላወስ አቃተኝ
ተደናበርኩልሽ ጥይት እንደሳተኝ
ሳተና ነበርኩኝ ተካሽ በመዉ ዛሬ
ለዘበናይ ብቻ እጄን ሰጠሁ ዛሬ

አዝማች

በሳሪያን ኮት ላይ ያንን ቀጭን ኩታ ጣል አድርጌ
በመኮንን ድልድይ ልምጣ በደረጃዉ በፒያሳ አድርጌ
እንደ አውራ ዶሮ ክንፍ ኮቴን እየሳብኩት መሬት ለመሬት
በዞርኩት ገላሽን ሳትወጣብኝ ፀሀይ ሳይነጋብኝ ሌት

ሲመሽ ወደማታ ማታ ማታ
አቤት ያንቺ ፍቅር ሲበረታ
ሲመሽ ወደ ማታ ማታ ማታ
ብቅ በይ ሲገረፍ ክራር ሲመታ

ማታ ማታ
ማታ ማታ

ሞልቶ በአራዳ የአርመን ዳቦ
ሳሳ አካላቴ ሰዉ ተርቦ
አቅፎ ገላዉን አልጠገብ ያለዉ
ማነዉ ብላችሁ ማነዉ ማነዉ?

ልቤ ልቤነዉ ልቤ እራብተኛዉ
እሳን ወዶ ሌት የማይተኛዉ
ይዉጣ ይዉጣ እግሬ ይዛል በእርምጃዉ
ከሏ አይብስም ሰባ ደረጃዉ

ዘበናይ ዘበናይ….

አይወጣም ደረጃ ቢፈጥን ሴሼንቶ
እንደኔ ካሌደ በፍቅር ተገፍቶ

ታም-ታራራም-ታራራም…..

መድፈሪያሽ ወርቅ ነዉ ብርም አይገዛሽ
ልብ የሌለዉ ሀብል ግድም አይሰጥሽ

ታም-ታራራም-ታራራም…..

ከአንገትሽ ላይ አርጊኝ እንደማርትሬዛ
ወደወዲያ እንዳልል አደብ እንድገዛ
ተከለከለ አሉ የንጉስ አዳራሽ
የክት ያለበሰ አይገባም በጭራሽ
መጣሁ ከኮሪያ ይዤልሽ ሰዓት
በፓሪ ሞድሽ ላይ አምርሽ ታዪበት

ዘበናይ ዘበናይ….

ግጥምና ዜማ፡ ቴዎድሮስ ካሳሁን (ቴዲ አፍሮ)
ሙዚቃ ቅንብር፣ ሚክሲንግ፣ ኪቦርድ እና ቤዝ ጊታር፡ ዳግማዊ ዓሊ
ናሙና ዝግጅት፡ አብርሃም ዘዉዴ
ክራር፡ ታመነ መኮንን
ድምጵ ቀረጳ፡ ክብረት ዘ/ኪዮስ
ፕሮዲዩስድ፡ በቴዎድሮስ ካሳሁን (ቴዲ አፍሮ)
አዲሱ የቴዲ አፍሮ “በ70 ደረጃ” ነጠላ ዜማ ሙሉ የዘፈን ግጥም

Health: የመንትዮች ነገር!

$
0
0

መንትዮችን ማየት በአገራችንም ይሁን በተቀረው ዓለም ክፍል የተለመደ ነው፡፡ ይሁንና ከተለመደው በተለየ የቆዳ ቀለም እና አፈጣጠር ዓለምን የሚቀላቀሉ መንትዮች የበርካቶችን ትኩረት ያገኛሉ፣ መነጋገሪያም ይሆናሉ፡፡ ሳይንቲስቶችና የዘርፉ ባለሙያዎችም ይህን የተፈጥሮ ምስጢር ለመፍታት በርካታ ጥናቶችን ያደርጋሉ፤ እንቆቅልሹንም ለመፍታት ይጥራሉ፡፡ እነዚህ አስገራሚ ክስተቶች የሚታዩበትን የመንትዮች ዓለም የተለያዩ ክስተቶችን ከባለሞያዎች አስተያየትና የሳይንስ ሰዎች ትንታኔ ጋር አጣምሮ ተከታዩ ዳሰሳችን ቅኝቱን ያሳያችኋል፡፡

Twins
እ.ኤ.አ ሚያዚያ 2005 ላይ ጥንዶቹ ብሪታኒያውያን ካይሊ ሆድሰን ከባለቤቷ ሬማ ጋር ወደ ሆስፒታል በምጥ ምክንያት ሲያመሩ ካይሊ በሰላም መገላገሏን እንጂ ስለወለደችው ልጅ የምታስብበት ብርታት አልነበራትም፡፡ ካይሊ የተገላገለችው መንታ ልጆችን መሆኑ ተገልፆላት እንድታቅፋቸው ሲሰጧት ግን ጉልበቷን አሰባስባ በግርምት ነበር የተቀበለቻቸው፡፡ እርሷ ብቻ ሳትሆን መላው ዓለም በዜናው ተገርሞ ነበር፡፡ የተወልዱት ሁለት ልጆች ሴት ህፃናት ሲሆኑ አንደኛዋ ጥቁር መልክ ያላት፣ ሁለተኛዋ ደግሞ ነጭ ነበረች፡፡

የህፃናቱ ወላጆች ራሳቸው ከነጭና ጥቁር ወላጆች የተገኙ በመሆናቸው መልካቸው የክልስ እና በጥቁር እና ነጭ የሚመደብ የነበረ ቢሆንም የሚወልዷቸው ህፃናት እንዲህ ሙሉ ለሙሉ የተለያየ የቆዳ ቀለም ይኖራቸዋል ብለው አስበው አያውቁም፡፡ በወቅቱ ጋርዲያን ለተሰኘው የእንግሊዝ ጋዜጣ ሀሳቧን ያካፈለችው ካይሊ ‹‹የልጆቼን ቀለም ስመለከት በጣም ነበር የደነገጥኩት፡፡ ነገር ግን በጣም የሚያማምሩ ሴት ህፃናትን ማግኘቴ ሁሉንም ወዲያው አስረስቶኛል፤ ደስተኛም ሆኛለሁ›› ብላ ነበር፡፡

ክስተቱን አስመልክቶ ባለሙያዎች ሳይንሳዊ ትንታኔን ሰጥተውበት ነበር፡፡ አንዲት ሴት የተቀላቀለ ዝርያ ካላት በእንቁላሎቹ ጥቁርም ሆነ ነጭ የቆዳ ቀለምን የሚያስገኙ ጂኖችን ቀላቅላ ትይዛለች፡፡ በተመሳሳይ ከነጭና ጥቁር ወላጆች የተወለደ ወንድ እንዲሁ በዘር ፈሳሹ ውስጥ ሁለቱንም የያዙ ጂኖች ይኖሩታል፡፡ የዘር ፈሳሹ ውስጥ የያዛቸው ጂኖች በሙሉ ነጭ ቢሆኑ እና ተመሳሳይ ጂኖች ያሉት እንቁላል ጋር ቢገናኙ አለዚያም ጥቁር ቀለምን ኮድ የሚያደርግ ስፐርም ከተመሳሳይ እንቁላል ጋር ቢገናኝ ቀለማቸው ሙሉ በሙሉ የተለየ የጥቁር እና ነጭ ልጆች በመንታነት ይወለዳሉ፡፡ ይህ የመፈጠር ዕድል ከሚሊዮን አንድ ጊዜ ያህል ነው፡፡ በእነ ካይሊ የተከሰተውም ይህ ነበር፡፡

ይህን መሰል አስገራሚ የመንትዮች ታሪኮች አልፎ አልፎ መሰማታቸው አልቀረም፡፡ ቀደም ሲል የነበረው አይነት ታሪክ ያላቸው ሰዎችም ጥቂት አይደሉም፡፡ እዚያው እንግሊዝ ውስጥ ከሰባት ዓመት በፊት መንትዮችን የወለዱ ቅልቅል ዝርያ የነበራቸው ወላጆች ለሁለተኛ ጊዜ ሲወልዱም አንድ ጥቁርና አንድ ነጭ ህፃናትን አግኝተዋል፡፡ በድምሩም የሁለት ጥቁር እና ሁለት ነጭ ልጆች ወላጆች ሆነዋል፡፡ ዲን ዱራንት የልጆቹ አባት ሲሆን ኦሊሳን ስፑነር ደግሞ እናቲቱ ነች፡፡ ጊዜው እ.ኤ.አ ሐምሌ 2008 ላይ ነበር፡፡ ‹‹በአምላክ ጥበብ ተደንቀናል ብሏል›› አባትየው ዲን ዱራንት፡፡ ከጀርመናዊ አባት እና ጋናዊት እናት እ.ኤ.አ 2008 እንዲሁ አንድ ነጭ እና አንድ ጥቁር ተወልደዋል፡፡ በዚህ መሰል አስገራሚ ታሪክ የታጀበው የመንትዮች ዓለም ላይ ሳይንስ የራሱን ትንተና ይሰጣል፡፡

አስገራሚው የመንትዮች ዓለም

መንትያ የሚለውን ቃል ባለሞያዎቹ ሲፈቱት በአንድ እርግዝና የተወለዱ ከአንድ በላይ ልጆች ይሉታል፡፡ ጥንቅር ይዘው በመልክም ሳይመሳሰሉ የሚወለዱ መንትዮች ‹‹ፍራተርናል›› የሚባሉት ሲሆን ሁሉም ነገራቸው አንድ አይነት ሆነው የሚወለዱት ደግሞ ‹‹አይደንቲካል›› ይሰኛሉ፡፡ ፍራተርናል የሚባሉት መንትያዎች የሚፈጠሩት የሴቷ ሁለት እንቁላሎች በሁለት ስፐርም ህዋሳት በተናጥል ሲሰበሩ እና ሲዋሃዱ ነው፡፡ በዚህ መልክ የሚፈጠሩ መንትዮች የዘረ መል ጥንቅራቸው የመመሳሰል ዕድሉ ዝቅተኛ ሲሆን በተለይ ዕድሜያቸው ከ35 በላይ በሆናቸው እናቶች ይህ አይነት መንትዮችን የመውለድ አጋጣሚያቸው ከፍ ያለ መሆኑን ባለሞያዎች ይናገራሉ፡፡

ሁሉ ነገራቸው አንድ አይነት ሆነው የሚፀነሱ እና የሚወለዱ መንትዮች የሚፀነሱት አንድ እንቁላል አንድ ውሁድ ሲፈጥርና ይኸው ውህድ ወደ ሁለት ተከፍሎ ሁለት ፅንስ ሲሆን ነው፡፡ የሚወለዱት መንትያ ህፃናት ‹‹አይደንቲካል ትዊንስ›› የሚባሉት ይሆናሉ፡፡ በዓለም አቀፍ ደረጃ ከ10 ሚሊዮን የሚበልጡ በዚህ መሰሉ አፈጣጠር የመጡ መንትዮች እንዳሉ አንዳንድ ግምቶች ያሳያሉ፡፡ በየዓመቱ ከሚወለዱ 1 ሺ ህፃናት መካከል 3 የሚደርሱት አንድ አይነት መንትዮች ይሆናሉ፡፡ ታዲያ መንትዮች ሲወለዱ ሁል ጊዜም ተመሳስለው አሊያም አንድ አይነት ሆነው ይወለዳሉ ማለት አይደለም፡፡ ከተለመደው ወጣ ያለ አፈጣጠር ያላቸው በቁጥርም በአይነትም የሚደንቁ ውልደቶች በየጊዜው ይሰማሉ፡፡ ከሁለት እስከ አስራ ሁለት ህፃናትን አንድ ጊዜ መውለድ፣ አፈጣጠራቸው አንዱ ከአንድ የተጣበቀ አሊያም የዘረመል ጥንቅሩን ካደገ በኋላ እንደገና ከእናቱ አሊያም ከፅንሱ የሚወስድበትን ሁኔታ ሳይንቲስቶች ተመልክተው ትንታኔ ይሰጡባቸዋል፡፡

ተጣብቀው የሚወለዱ መንትዮች

የሁለቱ ወላጆች ዘር ማስተላለፊያ የሆኑት እንቁላልና ስፐርም ተቀላቅለው ውህድን ፈጥረው ወደ ሁለት ፅንስነት (መንትያነት) ለመለወጥ በአማካይ ፅንሱ ከተፈጠረ ጀምሮ 8 ቀናትን ይፈልጋሉ፡፡ ይህ 99 ከመቶ የሚሆኑት ላይ በመደበኛነት የሚፈጠር ነው፡፡ ይህ ሳይሆን ቀርቶ ፅንሱ ለሁለት ለመክፈል ከ8 ቀናት በላይ ከወሰደ ግን ፅንሶቹ ተጣብቀው የማደግና የመወለድ አጋጣሚ ዕጣቸው ይሆናል፡፡ የተጣበቁ ፅንሶች አካላትን ይጋራሉ፣ ተያያዥ ችግሮች ሞቶ እስከመወለድ በሚደርስ አደጋ የመከሰት ዕድሉ ከፍ ያለ መሆኑንም ስፔሻሊስቶቹ ይናገራሉ፡፡ ይህን መሰል እርግዝና ከ50,000 ሴቶች በአንዷ ላይ እንደሚከሰት ግምታቸውን የሚያስቀምጡ ባለሞያዎች እነዚህ ተጣብቀው የሚወለዱ ህፃናት እንደ ጭንቅላት፣ ልብ እና ጉብት የመሰሉ አካላትን የሚጋራ ሲሆን እነርሱን መለያየቱ ከባድ ፈተና ይሆናል ባይ ናቸው፡፡ ‹‹የሁለቱንም ህፃናት ነፍስ ማትረፍም ትልቅ ጥበብ ብቻ ሳይሆን እድለኛ መሆንንም ይጠይቃል›› ይላሉ ታዋቂው የአሜሪካ ተቋም ማዮ ክሊኒክ ባለሙያ ዶ/ር ሉሲ ጋርፊልድ፡፡ ‹‹ስኬታማ መንትዮችን የመነጣጠል ቀዶ ጥገና ሲካሄድ ዓለም አቀፍ መገናኛ ብዙሃን የሚቀባበሉትም ለዚህ ነው››

ሌሎች አስገራሚ አፈጣጠሮች ኪመሪዚም፣ ፓራሲቲዝም…

ሌላው በመንትያነት በሚያድጉ ፅንሶች መሀል ከሚከሰቱ ለየት ያሉ አፈጣጠሮች የሚመደበው ከአካላቶቻቸው መካከል አንድ ወይም ሌላውን አብሮት ካለው መንትያ ፅንስ አሊያም ከእናትየው ወስደው በመቀላቀል ለየት ያለ ህብር ያለው የቆዳ ቀለም የሚያበጁ፣ ፆታቸው ወንድ ወይም ሴት መሆኑን ቁርጥ አድርጎ ለመለየት የሚያስቸግር ብልት ያላቸው እና መሰል አፈጣጠርን የሚያሳዩ ናቸው፡፡ በሳይንሱ አጠራር ይህ ክስተት ኪመሪዝም ተብሎ ይጠራል፡፡

አንድ ፅንስ የዕድገት ዘመኑን ሲጀምር አንዳንድ ጊዜ በመንታነት ሊጀምር ይችላል፡፡ ነገር ግን ሌሎቹ ተስፋ ያላቸው የእንቁላል እና ስፐርም ውህዶች ሲሞቱ አንድ ብቻ ትግሉን አሸንፎ አንድ ፅንስ ሆኖ ልጅ ሆኖ ይወለዳል፡፡ እንዲያውም ተመራማሪዎች የሚገምቱት በአንድ ወሲብ ግንኙነት እስከ 8 የሚደርሱ ፅንሶች የመፈጠር ዕድል እንዳላቸው ነው፡፡ ነገር ግን ሙሉ ጊዜውን ጨርሶ ህይወት ዘርቶ የሚወለደው አንድ ብቻ ይሆናል ሲሉ ግምታቸውን ያስቀምጣሉ፡፡ ሌሎቹ የተደመሩ ፅንሶች ሲሞቱ አንድ በርትቶ ህይወት የሚሆንበትን ይህን አጋጣሚም ‹‹ቫኒሺንግ ትዊን ሲንድሮም›› ሲሉ ይጠሩታል፡፡

አንዱ ፅንስ ለሌላኛው እየመገበ ተጎድቶ የሚሞትበት፣ አንዱ መንትያ አስርዷት ሁለተኛውን አምጣ ጤነኛ ልጅ እናት የምትወልድበት እና ሌሎችም ከመንትያ ፅንስ እና ልጆች ጋር የተያያዙ ክስተቶች የማህፀንና ፅንስ ስፔሻሊስቶችን እና ተመራማሪዎችን ትኩረት የሚይዙና ልዩ ምርምሮችም የሚካሄድባቸው አስገራሚ የተፈጥሮ ሁነቶች መሆናቸው በተመራማሪዎቹ ይገለፃል፡፡

ተጣብቀው የተወለዱት ኢትዮጵያውያን
አገራችን ውስጥ በጥቁር አንበሳ ሆስፒታል የተመዘገበ ታሪክን የሆስፒታሉ ባለሙያዎች እ.ኤ.አ 2005 ላይ በኢትዮጵያ ሜዲካል ጆርናል ላይ አሳትመው አቅርበውት ነበር፡፡ ከ25 ዓመት እናት የተወለዱት መንትዮች ደረታቸው ላይ ተጣብቀው የተወለዱ ሲሆን ይህም አጥኚዎቹ እንዳሉት በአገሪቱ የገጠመው ለሁለተኛ ጊዜ ነበር፡፡ በቀዶ ጥገና መንትዮቹ ተለያይተዋል፡፡ ከጥቁር እና ነጭ መንትዮቹ አንስቶ ተጣብቀው እስከሚወለዱት እንዲሁም ምግብ ጥገኛ ሆነው እስከሚጠፋፉት ድረስ የመንትዮች ታሪክ አስገራሚ ነው፡፡ ይህ ተወልደውም ይቀጥላል…

የመንትዮች ቆጠራ
እ.ኤ.አ 2006 ላይ የዩናይትድ ስቴትስ ተመራማሪዎች ባደረጉት ጥናት በዓለም አቀፍ ደረጃ 125 ሚሊዮን የሚደርሱ መንትዮች በህይወት እንደሚገኙ ጠቁመዋል፡፡ ይህም ከአጠቃላዩ የዓለም ህዝብ 1.9 ከመቶ መያዛቸውን ያመለክታል፡፡ የመንትዮች እርግዝና ከመደበኛው እርግዝና ቢያንስ በ3 ሳምንት ቀድመው ልጆቹ እንዲወለዱ ያስገድዳል፡፡ ከጊዜያቸው ቀድመው መወለዳቸው የጤና እክልን የማስከተል ዕድል ስላለው ጥብቅ የህክምና ክትትልን ይሻሉ፡፡

ናይጄሪያ የመንትዮች መናኸሪያ
በዓለም ላይ ከሚወለዱ 90 ህፃናት አንዱ በመንትያነት የተወለደ እንደሚሆን የመንግስታቱ ድርጅት ፖፑሌሽ ቢሮ ይገምታል፡፡ በተለይ ከፍተኛውን የመንትዮች ቁጥር በማስመዝገብ የምዕራብ አፍሪካዊቷ አገር ናይጄሪያ ቀዳሚ ናት፡፡ ዮሩባ በምትባለው የናይጄሪያ ግዛት ከ1,000 ህፃናት መካከል 45 የሚወለዱት በመንትያነት ነው፡፡ አንዳንድ ተመራማሪዎች በናይጄሪያ ዩሩባ ግዛት መንትዮች የበረከቱበትን ምክንያት በግዛቲቱ ሰዎች ከሚበሉት አንድ ጣፋጭ ተክል ጋር አያይዘውታል፡፡ ዲዮስኮሪያ ሮቱንዳታ የተሰኘው ይህ ጣፋጭ በውስጡ ፋይቶ ኤስትሮጅን የሚባል ንጥረ ነገር ሴቶች ከእንቁላል ማምረቻቸው ሁለቱም ጎን እንቁላል እንዲያመርቱ እና ሁለት ፅንስ እንዲፈጠር አድርጓል ሲሉ ይከራከራሉ፡፡ ናይጄሪያን ተከትላ ሊንሃ ለአፔድሮ የተሰኘችው የብራዚል አነስተኛ መንደር ትጠቀሳለች፡፡ በዚህች መንደር ከሚፈጠሩ እርግዝናዎች 10 ከመቶ የሚሆኑት መንትዮችን ይወልዳሉ፡፡

መንትዮችን መውለድ ስንት ሰዓት ይፈጃል?
መንትዮችን ማርገዝ ብቻ ሳይሆን መውለድም ታዲያ ቀላል አይሆንም፡፡ ምጥ የተለመደ የነፍሰጡሮች ፈተና መሆኑን የሚያውቁት ባለሙያዎች ግን በዚህ ሳያበቁ ‹‹መንትዮችን መውለድ ስንት ደቂቃ ይፈጃል?›› ሲሉ ጥናት አድርገው በአንድ የጥናት መፅሔት ላይ ውጤታቸውን አሳትመው ነበር፡፡ በተለይ በጀርመን የተካሄደው 15 ዓመታትን የፈጀ ጥናት 8,220 ወላጆች መንትያ ልጆች ሲወልዱ የፈጀባቸውን ሰዓት መዝግቦ ተንትኗል፡፡ በዚህ ጥናት እንደተመለከተው መንትዮችን የምትወልድ እናት በአማካይ ለ13 ደቂቃ አምጣለች፡፡
75 ከመቶ የሚሆኑት በ15 ደቂቃ ውስጥ ዱብ ሲያደርጉ 23 ከመቶዎቹ ከ15 ደቂቃ እስከ 1 ሰዓት ወስዶባቸዋል፡፡ 2 ከመቶዎቹ ደግሞ ከአንድ ሰዓት በላይ አምጠው መንትያዎቻቸውን ተገላግለዋል፡፡
መንትዮችን መፀነስ ብቻ ሳይሆን መውለድም ፈተና መሆኑን ያሳዩት ጥናቶች አንዲት ሴት መንትያ ልትወልድ የምትችልባቸውን እድሎች እና አጋጣሚዎች ከታሪካዊ ዳራዎችና ሳይንሳዊ ትንታኔዎች በመነሳት ግምት አስቀምጠዋል፡፡ እነዚህ መንታ በመውለድ እድል ውስጥ ይከታሉ ከተባሉት ምክንያቶች መካከል ጥቂቶቹ የሚከተሉት ናቸው፡፡
- የምዕራብ አፍሪካ በተለይ የዮሩባ ዘር ካለባት
- ዕድሜዋ ከ30-40 ከሆነ
- በአካል የበለጠ ቁመት እና ክብደት ካላት
- ከዚህ ቀድሞ በተደጋጋሚ አርግዛ የምታውቅ ከሆነ
- መፀነስ የሚያስችሉ ሕክምናዎችን የምትወስድ ከሆነ
እርስዎ ከላይ የተዘረዘሩት ምድብ ምክንያቶች ውስጥ ገብተው ይሆን? አምላክ የእርስዎ በረከት ይሁን ካለው ፀጋውን መቀበል እና መደሰት እንጂ ምን ያደርጋሉ?

‹‹ይድረስ ላንቺ›› ተፃፈ ከስድስተኛ ተከሳሽ –በዘላለም ክብረት

$
0
0

‹‹ይድረስ ላንቺ››
ተፃፈ ከስድስተኛ ተከሳሽ
በዘላለም ክብረት

ወዳጄ ልቤ ከቶ እንደምንድን ነሽ? እውን እኔና አንቺ በአለም ስንኖር ሌላ የመገናኛ ዘዴ አጥተን ወደ snail mail እንመላለሳለን ብለሽ አስበሽ ታውቂያለሽ? ለማንኛውም እንዲህ ሆነ፡፡ ጥጋበኛ ሰው ያስቀናኝ ጀምሮልሻል፣ ጥጋበኛ እንዲህ የሚለው ትዝ አለኝ፡፡

‹‹ ….ደብዳቤ ቢጽፉት እንደ ቃል አይሆንም፣
እንገናኝ እና ልንገርሽ ሁሉንም….››
zelalem
የደላው! ቢያሻው በደብዳቤ፣ ሲፈልግ በአካል እያማረጠ እኮ ነው፡፡ ለእኔ አሁን ባለሁበት ሁኔታ ሁለቱም ቅንጦት ነው (ወይ ደብዳቤው አይደርስሽም ወይም አንቺን ማየቴ ሊገደብ ይችላል)፡፡ ቆይ ትንሽ የጎን ወሬ ላዋራሽና ምክንያቱን እነግርሻለሁ፡፡ ‹‹አንቺ›› ተብለሽ በዚህ ደብዳቤ ስለተጠቀስሽው ‹‹አንቺ››ና ይሄን ደብዳቤ ለሚያነቡ ወዳጆች የዕምነት ክህደት ቃሌን በትንሹ ላስፍር፡፡

እመቤት ሲልቪያ ፓንክረስት የኢትዮጵያ ፍቅረኛ (Ethiopian by choice) ዱቼ ሞሶሎኒ እትዮጵያን በወረረ ጊዜ፤ ወራሪው ሃይል በመላው ኢትዮጵያ ‹‹ የኢትዮጵያን ስም እያነሱ መፃፍ ክልክል ነው›› የሚል ያልተፃፈ አዋጅ አውጆ እንደነበር ይነግሩናል፡፡ በዚህም ምክንያት ፀሀፍቱና አዝማሪያኑ ስውር መጠሪያ መጠቀም ስላስፈለጋቸው እስከ ዛሬ ድረስ ተወዳጁ ሕዝባዊ ዘፈን አንቺ ልጅ አንቺ ልጅ እንደ ስውር የፍቅር ዘፈን ተበርክቷል፡፡ በዘፈኑ ‹‹አንቺ ልጅ ›› የተባለችውም ኢትዮጵያ ናት፡፡ እኔስ በዚህ ዘመን ‹ይድረስ ለባለ ታሪኩ›፣ ‹ይድረስ ለባለ ንብረቱ›… እንደሱ የሀዘን ደብዳቤ ርእስ ‹ይድረስ ለኢትዮጵያ › በማለት ፋንታ ‹ይድረስ ለአንቺ› ለማለት ስውር መጠሪያ ተጠቅሜያለሁ? ፤ በፍፁም! ጌቶች እንደሚሉት ሕገ መንግስቱ የመናገር ነፃነቴን ሙሉ ለሙሉ አስከብሮልኛልናi
ቧልቱ ይቆየንና በዚህ ደብዳቤ ርዕስ ዙሪያ ያለማንም አስገዳጅነት የእምነት ክህደት ቃሌን ላስፍር አንቺ የተባለችው ኢትዮጵያ አይደለችም፡፡ ‹አንቺ› የኔዋ ሀቢቢ ግን ባለሽበት ይድረስሽ፡፡ ውዴ እንግዲህ በዚህ ደብዳቤ ያለፈውን እያነሳሁ እነግርሻለሁ፡፡ወይ ትስቂያለሽ (ሳቅሽ እንዴት ያምራል?) ወይ ደግሞ ታዝኛለሽ (እኔን!)

ይህንን ደብዳቤ የመፃፍ መብት
እነሆ ላንቺ ስለሆነው ሁሉ ላጫውትሽ ስጀምር፤ በመነሻው ያሰብኩት ነገር ይሄን ደብዳቤ የመፃፍ ሕጋዊ መብት አለኝን? የሚለውን ጥያቄ ነው፡፡ ለዚህም መነሻዬ አሁን ያለሁበት ሁኔታ ነው፡፡ በመጀመሪያ “ሕገ-መንግስታዊ ስርአቱንና ሕገ-መንግስቱን በሀይል ፣በዛቻና በአድማ ለመናድ በመምከር/ በመናድ” ወንጀል ተጠርጥሬ የታሰርኩ ቢሆንም፤ በታሰርኩ በ23ኛው ቀን ወንጀል ወንጀልን፤ ጥርጣሬ ሌላ ጥርጣሬን እየወለደ የተለያዩ የሽብር ተግባራትን ለመፈፀም ለማሴርና ለማነሳሳት ወንጀል ተጨማሪ ጥርጣሬ በፓሊስ ዘንድ በማሳደሬ የክፋት ልኬ ከፍ ያለ ሲሆን፤ በመጨረሻም ሕገ-መንግስቱን እንደ እያሪኮ ግንብ ለመናድ በመሞከር፤ ሕብረተሰቡን ደግሞ ከሚተነፍሱት የሰላም አየር ለማቆራረጥ ከማሰብ የተለያዩ የሽብር ተግባራትን ለመፈፀም ሲንቀሳቀስ ተይዟል በሚል ወንጀሎች ተከስሼ በማረፊያ ቤት እገኛለሁ፡፡ ይሄን ሁሉ የምነግርሽ ‹ለ አንቺ› አዲስ ነገር ነው በማለት አይደለም፡፡ ይልቁንስ ያለሁበት የእስር ሁኔታ ደብዳቤ ካንቺ ጋር እንዳልፃፃፍ ይከለክለኛልን? የሚለውን ለማስረዳት በማሰብ ነው፡፡

መቼም አሁን ያለሁበት ሁኔታ ተገቢ ነው ብዬ ባላምንም ‹ ዋስ ጠበቃዬ ነውና› ስለመብቴ ስናገር ያን የፈረደበት ህግ መጥቀሴ አልቀረም፡፡ ታዲያስ በእስር ላይ ያለ ሰው ከወዳጁና በሕይወቱ ጋር ደብዳቤ ሊፃፃፍ ምን ገደብ አለበት? ይላል ስል፤ ስለፌደራል ታራሚዎች አያያዝ የወጣ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ ቁጥር 138/1999 በአንቀፅ 18 ላይ “ታራሚዎች (ተጠርጣሪዎች) ከማረሚያ ቤቱ (ከማረፊያ ቤቱ) ውጭ ካሉ ሰዎች ጋር መፃፃፍ ይፈቀድላቸዋል፡፡ ሆኖም ለጥበቃ ስራ ተቃራኒ የሆነ ተግባር እንዳይፈፀም በፅሁፎቹ ላይ ቁጥጥር ይደረጋል” በማለት የኔና አንቺ ደብዳቤ መፃፃፍ በሕግ የተፈቀደ ነገር እንደሆነ ደንግጎልናል፡፡ አሜን! (እንዲያው ይሄ ልጅ አሁንስ ተስፋዬ.. ማነው ? ሕጉ አይደለምን… የሚል የጅል ዘፈኑን አላቆምም እንዴ? ብለሽ እንደማታሾፊብኝ እምነቴ ነው) ጓድ ሌኒን በዛች የፒተርስበርግ እስር ቤት ውስጥ ደብዳቤ መፃፃፍ አትችልም ተብሎ ተከለከለ እርሱ ግን የ Russia Social Democratic Party ን ፕሮግራም መፅሀፍ ውስጥ በየመስመሮቹ መሀል በ Invisible Ink በመፃፍ ታሪክ ስራ፡፡ እነሆ እኔ ግን በትናንት ሌኒኒስቶች (ፋና)፤ በዛሬ አሳሪዎቻችን መልካም ፈቃድ ደብዳቤ የመፃፃፍ ሕጋዊ መብቴ ተከብሮልኝ ይሔው በነጩ ወረቀት ላይ እንደ ሕዳሴው ባቡር እፈነጭበታለሁ፡፡

እንዲህ ሆነልሽ
አበባዬ- አፄ ሀይለስላሴ ከማንኛውም ባለስልጣን በሕይወት ዘመናቸው የበለጠ የቀረቧቸው የነበሩት ከ1934-1948 ድረስ ለ14 ዓመታት በፅህፈት ሚንስትርነት ያገለገሏቸውን ፀሀፊ ትዕዛዝ ወልደ ጊዎርጊስ ወልደ ዮሀንስን እንደ ነበር ነግሬሻለሁ? ወዳጅነትና ፍቅር ያልፋልና ሀይለስላሴና ወልደ ጊዎርጊስ ተጣሉ፡፡ የአፄ ሀይለስላሴ መንግስት መፅሀፍ ፀሀፊ አቶ ዘውዴ ረታ የወልደጊዎርጊስን መጨረሻ ሲተርኩ፡፡

‹‹ ፀሃያማው ሚያዚያ 17/1948 ቀን ለ ወልደ ጊዮርጊስ ወልደ ዮሀንስ እንደ ሌሎቹ ቀናት ብሩህ ሁና ነበር የነጋችው፡፡ ብሩህ ሁና እንደምታመሽም አልተጠራጠሩም ነበር፡፡ ምን ያደርጋል! ያች ክፉ ሰኞ የወልደጊዎርጊስ ከፍተኛ ስልጣን መጨረሻ ሆነች፡፡ በእኩለ ቀን ገደማ ቤተ መንግስት ተጠርተው ከፅህፈት ሚንስተርነታቸው ተነስተው የአሪሲ ጠቅላይግዛት ደረሳቸው››
(መፅሀፉ አጠገቤ ስለሌለ ቃል በቃል አልጠቀስኩም)

ወልደጊዮርጊስ ተሽረው ከቤተ-መንግስት እንዲርቁ የተደረገበት ምክንያት የሀይለስላሴን ወንበር በሰዒረ መንግስት ለመገልበጥ አስበዋል በሚል ምክንያት ነበር፡፡ወልደጊዎርጊስን እዚህ ጋር ማንሳቴ የሚያዚያ 17 ስለት እኔም ጋር በመድረሷ ነው፡፡ ውዴ! የእኔዋን ሚያዚያ 17/2006 ዓ.ም ውሎ እንደ ዘውዴ ረታ ስተርክልሽ ይሔን መሳይ ይሆናል፡፡

‹‹ ፀሃያማዋ ዓርብ ሜያዚያ 17/2006 ዓ.ም አጀማመር እንደ ወትሮው አልነበረም፡፡የጠዋት ትምህርት ክፍለ ጊዜ እንዳይረፍድብኝ እየተቻኮልኩ ወደማስተምርበት (የመጨረሻ ክላስ ነበር) አምቦ ዩንቨርሲቲ ስሄድ፤ ተማሪዎች አዲስ የተዘጋጀውን የአዲስ አበባ ከተማ መሪ እቅድ ‹ሕገ-መንግስታዊ አይደለም በሚል መነሻ የተለያዩ መፈክሮችን እያሰሙ ሰላማዊ ሰልፍ ወጥተው ነበር፡፡ ሰልፉ ሰላማዊ በሆነ መንገድ ተካሂዶ እንደተጠናቀቀ በሰልፍ ምክንያት የቀረውን የመጨረሻ ክላስ ሚያዚያ 18/2006 ዓ.ም ለማካሄድ ተማሪዎቼ ጋር ቀጠሮ ይዤ ብለይም ‹ሰው ያቅዳል ፣ እግዜር ይስቃል› እንደሚባለው ሆነና በዛች ሚያዚያ 17/2006 ዓ.ም ማምሻ ላይ እንደ ወልደጊዎርጊስ ወልደ ዮሃንስ ‹የመንግስትን ዙፋን በሕዝባዊ አመፅ ልትነጥቅ አሲረሀል› በሚል ክስ በቁጥጥር ስር እንደዋልኩ የደህንነት ግሪሳዎች (8 ወይም 9 የብሄራዊ መረጃና ደህንነት አባላት ) አበሰሩኝ፡፡

ነገሩ ብዙም አልገረመኝም፡፡ ትንሽ ያበሳጨኝ አቶ ዘላለም ለጥያቄ ስለምንፈልጎት አዲስ አበባ የፌደራል ወንጀል ምርመራ ዘርፍ (ማእከላዊ) ነገ ጠዋት 3 ሰዓት እንዲገኙ ብለው በስልክ ቢጠሩኝ ‹እሺ ነገ ሶስት ሰአት ላይ ክላስ አለኝ ከክላስ ወደ 9 ሰዓት አካባቢ አመጣለሁ › ብዬ የምቀርበውን ሰው ይሔን ሁሉ ሀይል ከሁለት መኪና ጋር በመመደብ ላከበረኝ መንግስቴ ‹ጉዳት› ባሰብኩ ግዜ ነው፡፡ ላክባሪዬ ውለታ መላሽ ያርገኝ i

ዓለሜ- ደብዳቤዬን እያነበብሽው እንደሆነ ተስፋ አለኝ፡፡ በቁጥጥር ስር ውሏል የምትለው ሀረግ ድሮም ትንሽ ፈገግ ታደርገኝ ነበር፤ አሁን ደሞ እኔን በቁጥጥር ስር ለማዋል ከአዲስ አበባ የመጣው የደህንነት ቡድን መሪ የመሰለኝ እድሜው ትንሽ ገፋ ያለ ሰው አንድ ሶስቴ ስልክ እየደወለ (ለማን ይሆን) ‹በቁጥጥር ስር አውለነዋል› እያለ መልክት ሲያስተላልፍ ስሰማ ፈገግ ማለቴ አልቀረም፡፡ ሀሳቤ ልቤ ፣ ይሄውልሽ ከስራ ቦታዬ ‹ሀገር ሰላም› ሕዝባዊ አመፅ ለመቀስቀስ አስበሃል በሚል ጥርጣሬ በቁጥጥር ስር የዋልኩት እንዲህ እንደገለፅኩት ነበር፡፡ ከሚያዚያ 17/2006 -ሀምሌ 11/2006 ዓ.ም ያሉት 84 ቀናት የተደጋገሙና ሕይወት አልባ በመሆናቸው እንዲሁ ከማሰለችሽ 5 ሁነቶችን ልፃፍልሽና ዘና በይ፡፡ ከሁነቶቹ በፊት ግን ስለ 84 ቀናቱ አጭር መግለጫ ልስጥሽ፡፡

የመጀመሪያዎቹን 75 ቀናት በፌደራል ወንጀል ምርመራ ዘርፍ (ማዕከላዊ) ጥብቅ ጥበቃ ክፍል (Siberia) ውስጥ 5 ቁጥር የተባለ 4 ሜትር በ5 ሜትር የሆነችና 5 ፍራሾችን በምትይዝ ክፍል ውስጥ ከረምኩ፡፡ ክፍሉ የተፈጥሮ ብርሀን በምንም አይነት መንገድ (ቀንን ጨምሮ) የማይገባበት ሲሆን፣ ለ24 ሰዓታት የመብራት ብርሀን ይበራበታል፣ መብራት ሲጠፋ በጄኔሬተር ሀይል ይተካል፡፡ ጄኔሬተሩ ነዳጅ ሲጨርስ ደግሞ ቀንም ሆነ ማታ ጨለማ ነው ባትሪ፣ ሻማ፣ ማንኛውንም አይነት ሰዓት መያዝ አይቻልም፡፡ ጠዋት 12 ላይ ለ10 ደቂቃ ፤ ማታ ከ10 ሰዓት አስከ 12 ሰዓት ለ 10 ደቂቃ ሽንት ቤት ለመጠቀም የክፍላችን በር የሚከፈት ሲሆን፤ በቀን ውስጥ ከ15 – 20 ደቂቃ ለሚሆን ጊዜ ደግሞ ከክፍላችን በየተራ ወጥተን ነፋስ/ፀሀይ እናየለን፡፡ ከዛ ውጭ በቀን ውስጥ ከ23 ለሚበልጠው ሰዓት የክፍሉ በር ዝግ ሲሆን ጮክ ብሎ ማውራትና መዝፈንም ቅጣት ያስከትላል፡፡

ወዳጄ በነዚህ 75 ቀናት ስንት ‹አሸባሪ› ወዳጆችን አፈራሁ መሰለሽ፡፡ መንግስቴ የ 15 እና የ14 ዓመት ልጆችን በአሸባሪነት ጠርጥሮ እንደሚያስርም ለመረዳት ችያለሁ፡፡ አብረውኝ በእስር የነበሩት ወዳጆቼ ጥርጣሬ አጅግ የተለየ ነው፡፡ ከአል-ሸባብ አስከ ኦብነግ እስከ ኦነግ እስከ የቤኒሻንጉል ጉምዝ ሕዝቦች ነፃ እውጭ ግንባር እስከ አቂዳ(አዲስ የሽብር ቡድን)… ስቃይን መማር ጥሩ ነውና ሁለት ለሚሆኑ ቀናት ብቻዬን በመታሰሬም solitary confinement ን experience ለማድረግ ‹ታድያለሁ›፡፡ በርግጥ ብቻዬን ታስሬ ነበር ከምል ካንቺ ሀሳብ ጋር ታሰርኩ ብል ይቀለኛል፡፡

አምስቱን ሁነቶች ዘንግቼ ስለ ስቃዬ ተንዛዛሁብሽ ይሆን? ለዚህ ተግባሬ በእስረኛ ቋንቋ ‹ተፀፅቻለሁ›፡፡ በቃ ወደ ጉዳዮቹ፡፡ ከዚህ በታች የምገልፃቸው ሁነቶች የ84 ቀናቱ የእስር ወቅት (የምርመራ) ጊዜ ምን እንደሚመስል እንደነበር ያስረዱሻል ብዬ አስባለሁ፡፡ (ሁሉም በእውነት እኔ ላይ የደረሱ ጉዳዮች ናቸው)፡

1. ተማሪዎቼን እንዳላበላሻቸው በማሰብ በቁጥጥር ስር ስላዋለኝ አመሰግናለሁ
ሚያዝያ 17/2006 ከምሽቱ 2 ሰዓት ጀምሮ ከምኖርበት አምቦ ከተማ ወደ አዲስ አበባ ከደህንነቶች ጋር በቤት አውቶሞቢል እየተጓዝኩ ነው፡፡ አንድ ልጅ እግር ደህንነት ጠየቀኝ
‹‹ዘላለም የህግ መምሕር ነህ አይደል..››
እኔ፡ አዎ
ደህንነቱ፡ “ስንት ጠበቆች ዳኞች ማፍራት ሲጠበቅብህ አንተ ‹ልማቱን ካላደናቀፍኩ› ማለትህ እጅግ ያሳዝናል፡፡ ለማንኛውም እንኳን ተማሪዎቹን ሳታበላሻቸው በጊዜ በቁጥጥር ስር ዋልክ፡፡ ኧረ ለመሆኑ ከውጭ ስንት ሽህ ደላዮችን አግኝተሻል? Any way በልማታችን ቀልድ የለም” አለኝ፡፡ (እኔም ባስተማርኩባቸው 4 አመታት ስንት ተማሪዎችን ‹እንዳበላሸሁ › እያሰብኩና ልማታችን በወለደው የአስፋልት መንገድ ፏ ብዬ ከምሽቱ 3፡50 ላይ ማዕከላዊ ከቸች፡፡

2. አላማችሁ ምንድን ነው?
እመቤቴ – መንግስት ሕዝባዊ አመፅ ለመቀስቀስ አሲራችኋል፤ ለዚህም በቂ ማስረጃ አለኝ በማለት ያሰረን ቢሆንም መንግስት ሀሳቡ እውነት ይሆንለት ዘንድ የእኛን ‹አዎ አሲረናል› የሚል መልስ በማባበልና በሀይል ለማግኘት ከመሞከር ውጭ ሌላ ያቀረበው አንዳችም ማስረጃም ሆነ መረጃ(በጠ/ሚንስትሮች ቋንቋ) አልነበረም/የለምም፡፡ ለዚህም ይመስላል በማእከላዊ የቆየሁባቸው ቀናት ምርመራው በሙሉ ‹አላማችሁ ምንድን ነው?› በሚል ሕይወት አልባና አሰልቺ ጥያቄ የተሞላው፡፡ እኔም የዚህ ጥያቄ ሰለባ ሁኜ ከረምኩልሽ፡፡ እንዲህ ላጫውትሽ፣
መርማሪ ፖሊስ (በተደጋጋሚ) – እንደ ዞን 9 አላማችሁ ምንድን ነው?
እኔ፡ ዓላማችን ግልፅ ነው፡፡ ማንም ብሎጋችንን የተመለከተ ሰው በቀላሉ ሊረዳው ይችላል፡፡ባጭሩ የተለያዩ ተረኮችን የሚያስተናግድ እና ሕብረተሰባዊ ተዋጾን የሚያሳድግ ፕሮፋይል ነው፡፡
መርማሪ ፖሊስ፡ እሱ ሽፋን ነው፤ እውነተኛ ዓላማችሁን ተናገር?
እኔ፡ ከዚህ የተለየ አላማ የለንም!

መርማሪ ፖሊሱ እንድንመልስለት የሚፈልገው ‹ከበላይ አካል› ይዞ እንዲመጣ የታዘዘውን መልስ፤ “አላማችን እንደ ጭቃ ተረግጦ፤ እንደ ገል ተቀጥቅጦ የሚገኘውን ጭቁን የኢትዮጵያ ሕዝብ ከተጫነበት ቀንበር ነፃ ማውጣት ነው፡፡ ለዚህም መሳካት ሕዝባዊ አመፅ ማደራጀትን እንደ ዋነኛ ዓላማ አድርገን ነው የተቋቋምነው፡፡”
ሲሆን ይህ ደግሞ ከአላማችን ጋር የማይገናኝ መንግስታዊ ፍላጎት በመሆኑ እንዲህ አይነት መልስ ከእኔ ማግኘት እንደማይችል የተረዳው መርማሪ በተደጋጋሚ አስብበት በማለት ይሰናበተኝ ነበር፡

3. ከመርማሪዎች ጋር የነበረኝ ቆይታ
የእኔ ፅጌሬዳ አላማችን እንደ ቡድን ባይጠይቁኝ ኑሮና የግል ዓላማዬን ቢጠይቁኝ አላማዬ ‹አንቺ› እንደሆንሽ ከመናገር ወደኋላ እንደማልል ታውቂያለሽ አይደል? የሆንሽ ‹አሸባሪ› ነገር፡፡ Any way ምርመራዬ ቀጥሎልኛል፡፡ ሁለት መርማሪዎች እየተፈራረቁ ገራሚ ገራሚ ጥያቄዎችን እየጠየቁኝ ነው፡፡ እነሆ ፡
መርማሪ ፖሊስ፡ ከአለም መሪዎች ማን ማንን አግኝተህ ታውቃለህ?
እኔ፡ ማንንም
መርማሪ ፖሊስ፡ እኛ እኮ ያለመረጃ አይደለም እየጠየቅን ያለነው፡፡ ጉድ ሳይመጣብህ ብትናገር ይሻላል፡፡
እኔ፡ እስኪ አስታውሱኝና ምን እንደተነጋገርን ልናገር፡፡ በርግጥ ባለፈው የኔልሰን ማንዴላ ማስታወሻ ፕሮግራም በ አፍሪካ ህብረት በተከበረበት ወቅት ጠ/ሚ ሀይለማርያም ደሳለኝ አግኝቻቸዋለሁ፡፡ ሌላ የማስታውሰው የለም፡፡
መርማሪ ፖሊስ፡ ህም! እሺ ዘንድሮ ኦባማ ፊት ንግግር ለማድረግ ከተመረጡ 3 ኢትዮጵያውያን አንዱ አንተ አይደለህም? አሜሪካ በ አፍሪካ ጉዳይ ምን አግብቷት ነው፡፡ ወጣት አመራሮች ምናምን እያለች የምታሰለጥነው?
እኔ፡ ‹‹እንዴ ኦባማ ፊት ንግግር ነው ያልከኝ? ድንገት ከታሰርኩ በኋላ ተመርጬ (በማሾፍ ድምፀት) ከሆነ አላውቅም፡፡ወይ በስም መመሳሰል ሊሆን ይችላል፡፡ አሜሪካ በአፍሪካ ጉዳይ ምን አግብቷት ነው? ላልከኝ ግን ወጣቶችን Empower ማድረግ ችግር ያለው አይመስለኝም ፤ ደግሞ በረሀቡም በድርቁም ጊዜ ርዳታ የምታደርገው እኮ አሜሪካ ነች፡፡ ምን አግብቷት ነው የምትረዳው አይባልም መቼም?!››
መርማሪ ፖሊስ፡ አሁን ዘመኑ የልማት ነው፤የምን ረሀብ ነው የምታወራው? በል ተወው፡፡

(‹ፈሪ ውሃ ውስጥ ያልበዋል› ሰምተሻል ውቤ? መንግስቴ ብቻውን እየሮጠም ፍርሃቱና ስጋቱ ብዛቱ፡፡ የሚቆጨኝ ነገር ከዓለም መሪዎች ማን ማንን አግኝተሃል? ‹ስባል› ከሲሪላንካ ፕሬዜዳንት ጋር ተገናኝቼ ወደ ደቡብ አሜሪካ ፔሩ በመጓዝ ማቹፒቹን ጎብኝቻለሁ ብዬ ብናገር ኑሮ፤ ክሳችን ላይ ‹ከሲሪላንካ መንግስት ባገኘው የገንዘብና የመሳሪያ ድጋፍ ወደ ፔሩ በመጓዝ ሕገ-መንግስት እንዴት እንደሚናድ በማቹፒቹ ኮረብታ ስልጠና ወስዶ ተመልሷል፡፡ ለዚህ እንደ ማስረጃ ይሆን ዘንድ ላፕቶፔ ውስጥ የተገኙት ከ300 በላይ የቼጉቬራ ምስሎችና Machu Pichu: The Mecca of Hippies” የሚል ባለ 22 ገጽ ‹ሰነድ› አብሮ ይያዝልኝ ነበር፡፡ ሲያበሳጭ

4. ‹አሸባሪው› ገብረሕይወት ባይከዳኝና ሀገሪቱን በሀራጅ የመሸጥ ጉዳይ
ፍቅር አደከምኩሽ አይደል?! ልጨርስ ስለሆነ ትንሽ ታገሺኝ፡ በዛውም ‹ፍቅር ታጋሽ ነው› የሚለውን Paulian ወንዴነት፤ ‹ፍቅር ታጋሽ ናት› በሚል ማስተካከያ እንድናርመው፡፡ የዚህ የምርመራ ነገር እኮ አላልቅልኝ አለ፡፡ በእስሬ ወቅት ሌላው በተደጋጋሚ እንዳስረዳ ስጨቀጨቅበት የነበረው ጉዳይ ‹ኒዮ-ሊብራልነቴና ልማትና ዲሞክራሲ ጎን ለጎን አብረው ይሄዳሉ ማለቴ ነበር፡፡
መርማሪ ፖሊሶቹ እየተቀያየሩ ስለኢህአዴግ የፖሊሲ ትክክለኛነት ‹ያስረዱኝ› ነበር፡፡ “አንተ ምን ጎደለብኝ ብለህ ነው ነጭ አምላኪ የሆንከው ? ትንሽ የተስፋ ጭላንጭል ስናይ አንተና ጓደኞችህ አይናችሁ ለምን እንደሚቀላ እስኪ ንገረን ? ይህች አባቶቻችን ‹በደምና በጾም› ያቆዩልንን አገር አንተና ያንተ ትውልድ ግን ውበቷ እና ድንቅነቷ ላስጎመጃቸው ነጮች ለመሸጥ መደራደር ጀመራችሁ….” እያሉ ‹በባንዳነት› ሲከሱኝ ከረሙ፡፡ የሀገሪቱ ውበትና የነጮች በውበቷ መጎምጀት ነገር ሲነሳ ጊዜ ‹አንቺ› ትስቂ ዘንድ የሚከተለውን አንቀፅ አሻግሬ ታደሰ የተባሉ ፀሐፊ ከ 50 ዓመት በፊት ‹እኔና አንተ› ካሉት ጽሁፋቸው ላይ እጠቅስልሻለሁ

“ኢትዮጵያ እጅግ ያማረች፤ የተዋበች ፤የተደነቀች፤ላያት ሁሉ የምታማልል፤የምታዘናጋ…….ናት፡፡ ዓይኗ የብር አሎሎ መለሎ ከአጥቢያ ኮከብ የተፎካከረ….. ነው፤ አገራችን ኢትዮጵያ ፅጌረዳ መስላ የሰኔን ቡቃያ ትመስላለች፡፡ የመስከረም አበባ ሆና በሩቅ ትስባለች፤የመስህቧ ኃይል ማግኔት ምስጋን ይንሳው፡፡ አገራችን ኢትዮጵያ ጥርሷ እንደ በረዶ ሆና ለፈገግታ ያህል ትንሽ ከንፈሯን ስትገልፀው እንኳንስ ለሰው ግብዙ መልዓክ ያብዳል፡፡ ኢትዮጵያ ፀጉሯ የሀር ነዶ ነው፤ኢትዮጵያ አጠረች ፤ረዘመች፤ወፈረች፤ብሎ ስለአካሏ መናገር አይቻልም፡፡ እንዲያው ዝም ይሻላል፡፡ በጠቅላላው ኢትዮጵያ ውበቷ ሰነፉን ይገድላል፡፡ ብርቱውን አነሁልሎ ያሳብዳል፡፡ እግዚአብሔር፤ኢትዮጵያን ሲፈጥር በብዙ ተራቋል፤ተጠቧል፤ ውበቷ በሩቅ ይስባል፤ አጥንትም ይሰብራል፤አዕምሮን ይሰውራል፡፡ ይገርማል!” ይላሉ፡፡

ምንም እንኳን ውበት እንደተመልካቹ ነው ቢባልም፤ መርማሪዎቹ በዚህ ዓይነት Vulgar Natioanlism ሰክረው እኔና የእኔ ትውልድ ሀገሪቱን ‹በውበቷ ለሰከሩ› ነጮች ልንሸጣት እንደተዋዋልን እየነገሩኝ ነው፡፡ ይገርማል! ዲሞክራሲን ከልማት እኩል ማስኬድ ነውር የለበትም፤ ተገቢም ነው ማለት እንደ አገር ሽያጭ ውል የሚቆጠርበት ብሎም ‹ሩቅ አስባ ሩቅ ለማደር እየተጋች ያለችን አገር› መንገድ ላይ በጠረባ ለመጣል የተደረገ ሙከራ ተደርጎ የሚወለድባትና ‹አሸባሪ› የምንሰኝባት፣ ‹ለፈገግታ ያህል ትንሽ ከንፈሯን ስትገልጠው እንኳን ሰውን ግብዙን መልዓክ የምታሳብደው ኢትዮጵያ!

ሊቁ ገብረሕይወት ባይከዳኝ ‹ልማትን ሲተች› “እውቀት በሌለው ሕዝብ አገር መንገድና የምድር ባቡር ቢሰራ ሕዝቡ እንዲደኸይ ያፋጥናል እንጂ አይጠቅመውም፡፡ ጥቅሙ ከርሱ ጋር የሚገበያዩ አዋቂ ሕዝቦች ነው” በማለት ‹ልማት ብቻውን ዋጋ የለውም› ሲል ይበይናል፡፡ ገብረሕይወት የእኛው ትውልድ አባል ቢሆን ኖሮ “የኢኮኖሚ እድገቱን በመካድ፤ ሕዝቡ በአዕምሮ መናወጥ ምክንያት የዘረጋነውን የባቡር ሀዲድ ፈነቃቅሎ እንዲጥልና ሌሎች የሽብር ተግባራትን እንዲፈፀም በማነሳሳት ‹ወንጀል›” መመርመሩና መከሰሱ አይቀሬ ነበር፡፡
ውዴ! ያን ‹አሸባሪ› ሳቅሽን ሳስብ በፀረ-ሽብር ሕጉ መሠረት ጉዳይሽ ሊታይ ይችላል የሚል ስጋቴ የበዛ ነው፡

5. ናፍቆቴ ሆይ!
እንዲያው ለዚህ 84 ቀናት ውስጥ የሆንኩትን ሁሉ እንዳልፅፍልሽ እንዳትሰለችብኝ ፈራሁ፡፡ እያንዳንዱን ሁነት በ Diary መልክ ከትቤ እንዳልክልሽ በነዛ ቀናት ውስጥ ብዕርም ሆነ ነጭ ወረቀት ይዞ መገኘት ‹ከፍ ብሎ አንገትን፣ ዝቅ ብሎ ባትን› ባያስቆርጥም ዛቻና ዱላን ማስከተሉ አይቀርም ነበርና ልከትብ አልቻልኩም፡፡ እንዲሁ በደፈናው ግን አንዳንድ ጉዳዮችን ብዘረዝርልሽ፡
በነዛ ክፉ ቀናት ከምሽቱ 12 ሰዓት እንቅልፍ መተኛትን ለመድኩ፡፡ ይሔም ነገር መልካም እንደሆነ አየሁ፡፡ ምክንያቱም ሌሊት ከእንቅልፍ ተቀስቅሰው ራቁታቸውን ሲደበደቡ አድረው ከ 3 እና 4 ሰዓታት ቆይታ በኋላ በነፍስ ወደ መኝታ ክፍላችን የሚመጡ የእስር ጓደኞቼን (Cellmates) ስቃይና ሰቆቃ ላለመስማት፡፡
በ2004 ዓ.ም የፌዴራል ፖሊስ ‘Cyber crime Laboratory’ ተቋቁሟል መባሉን ሰምቼ ‹እንግዲህ cyber criminal ሁሉ የት ትገቢ? አለቀልሽ!› ብዬ ነበር፡፡ በጊዜ ቀጠሮ ጊዜ እንደተረዳሁት ደግሞ ‹ያለችን አንዲት ኮምፒውተር ናት የእነዚህ ልጆች ዳታ በአንድ ኮምፒውተር መርምረን መጨረስ ስላልቻልን የጊዜ ቀጠሮ ይሰጠን› ሲባል ነው፡፡ አረ እንዲያውም ‹እስኪ Anti-virus ካለህ ኮምፒውተሬ ላይ ጫንልኝ› ተብዩ ሁሉ ነበር፡፡ ‹ለሽብር ተግባራት› መመርመሪያ ያልሆነ ‘Cyber crime laboratory’ ለመች ሊሆን ነው?
አንድ ቀኑንና ወሩን በማላስታውሰው ቀን አንድ ጎልማሳ የታሰርንበትን ክፍል አስከፍተው ገቡና እያንዳንዳችን መጠየቅ ጀመሩ፡
- ‹አንተ ከየት ነው የመጣኸው?› (አንድ ተማሪ ወዳጄን)
- ‹ከሀሮማያ ዩኒቨርስቲ›
- ‹አሀ እናንተ ናችኋ…..›
****
- ‹አንተኛውስ ከየት ነው የመጣኸው?!›
- ‹ከወለጋ ዩኒቨርስቲ›
- ‹አሁን ኦሮሚያ ብትለማ ምን የሚያስከፋ ነገር አለው?!….›
*****
- ‹አንተስ ከየት ነው የመጣኸው› (እኔን ነው)
- ‹ከአምቦ ዩኒቨርስቲ›
- ‹ሕዝቡን እርስ በርስ አጋጭታችሁ ከተማዋን በደም ያጠባችኋት እናንተ….›
- ‹አረ እኔ ከግጭቱ በፊት ነው የታሰርኩት›
- ‹በእውነት ነው የምልክ እድለኛ ነህ፡፡ የኦሮሚያን ልማት ተቃወመ ተብለህ በታሪክ አለመስፈርህ በጣም እድለኛ አድርጎሀል፡፡›
(ለመሳቅ ሁላችንም የጎልማሳውን ከክፍል መውጣት እየተጠባበቅን እኮ ነው ውዴ) – ሁሉ ቧልት የሆነበት ሀገር!

በነዚህ ሁሉ የጉድ ቀናት ለምን እንደታሰርኩ ትክክለኛውን ምክንያት የሚነግረኝ አካል ፍለጋ ሁሌም አስብ ነበር፡፡ መታሰሬ ግን አያስገርመኝም፤ አያስከፋኝም! ደስታን በሔድኩበት ሁሉ እፈልጋለሁ፤ የእድል ነገር ሆኖ ደስታም ከእኔ አይርቅም፡፡ ፍቅሬ ለረጅም ዘመናት ‹የሰው የመኖር አላማ ማወቅ ነው› የሚለውን Aristotlian (አሪስቶትሊያን) አስተምህሮ በልቤ ይዤ እኖር ነበር፤ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ግን ‹የመኖር ዓላማ መደሰት ነው› የሚለው አስተምህሮ በአርስቶትሉ ‹የማወቅ ዓላማ› ደባልቄ ይሔው እየተደሰትኩልሽና እያወቅሁልሽ እገኛለሁ፡፡ ‹አንች› የደስታዬ ምንጭ፡

‘‘Thanks to you….For you exist’
Clézio

ስለክሴና ስለተስፋዬ ሌላ ደብዳቤ እፅፍልሻለሁ፡፡
P.S አሳሪዬ ሆይ ልብ ይስጥህ!
ያንችው ዘላለም
ከብዙ ፍቅር ጋር!

Viewing all 15006 articles
Browse latest View live